EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ @infoematgurage Channel on Telegram

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

@infoematgurage


እማት ጉራጌ ፕሮጀክት በተስፋ ነዳ ሀሣብ አመንጪነት የተጀመረ የጉራጌንባህል ፣ ሙዚቃ ፣ ከተሞች ና የተ
ቱሪዝም ሀብቶች የማስተዋወቅ አላማ ያነገበ ፕሮጀክት ነው።

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ (Amharic)

በአማርኛnnእማት ጉራጌ ፕሮጀክት በተስፋ ነዳ ሀሣብ አመንጪነት የተጀመረ የጉራጌንባህል ፣ ሙዚቃ ፣ ከተሞች ና የተቱሪዝም ሀብቶች የማስተዋወቅ አላማ ያነገበ ፕሮጀክት ነው። እሳት ጉራጌ 'EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ' ተብዬን መልእክት ከታከለ በኋላ መስራት ጀምሮ የፕሮጀክት ቃለ አጠቃላይ መንገድ የማከለከሉ ያልተከተተሉ ቦታ ነው። እስቲት ከቀጣይ መረጃዎቹ አጣለ በመሰብሰቢዎቹ መሰረትን የቴሌግራም በትርንስር፣ ሙዝቃና ቻነሎች ያሉ ነገሮች እና ፕሮጀክት እንዲሁም ለውጥ የሚጠቀም አጋሮች ይኖራል።nnከሌሎቹ ፕሮጀክቶች መሰረት የምትሰጠዉ እና ድርጊቶቹ ከምንም የሚያስርጉት ማድረግ እና ማሳከስ በአማርኛ የቴሌግራም ማሳሰቢያ ነው።

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

11 Feb, 16:15


ወልቂጤ - ወርቅጥየ ❣️

ለምታውቋትም ለማታውቋትም ❣️

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

08 Feb, 17:25


አግዙን !
ለጉራጌ ዞን ሙሁር አክሊል ወረዳ መዘወር ትምህርት ቤት
* 2.9 ሚሊዮን ብር ያስፈልገናል!

#Ethiopia | በጉራጌ ዞን ሙሁር አክሊል ወረዳ መዘወር የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት ላለፉት 48 አመታት እያስተማረ በተለያየ መስክ ለሀገሪቱ የተማረ የሰዉ ሀይል እያፈራ ቆይቶአል፡፡

ሆኖም ለረዥም አመታት ትምህርት ቤቱ በአካባቢዉ ማህበረሰብ በአቶ ዋልጋ ምህረቱ ድጋፍ የነበረ ቢሆንም አቶ ዋልጋ ከዚህ አለም በሞት ከተለዩ በኃላ ትምህርት ቤት ይስፋ ከተባለ ወዲህ ትኩረት በማጣቱ ትምህርት ቤቱ የመፍረስ አደጋ ተጋርጠበት የአካባቢው ተወላጆች በጎ አሳቢዎች የቀድሞ ተማሪዎች ተረባርበው በአጭር ጊዜ ትምህርት ቤቱ ውስጥ ካለው 22 ክፍሎች ውስጥ 19 አድሰው 200 የተማሪዎች መቀመጫ ገዝተው እንዲሁም 10 ብላክቦርድ እና መጠነኛ እስቴሽነሪ በአንድ ወንድማችን በኩል ተማልቶ ከፈረሰበት ወጥቶ በአዲስ መልክ ማስተማር ጀምረዋል።

ሆኖም ተማሪዎች እጅግ የሚያሳዝኑ በአነስተኛ ግብርና የሚተዳደሩ የገጠር የገበሬ ልጆች ሲሆኑ ትምህርት ለነገ ህይወታቸዉ እጅግ ወሳኝ ነዉ።

ስለዚህ ትምህርት ቤቱ አስቸኳይ ማሟላት ያለባቸዉ ጉዳዮች ስላሉ የእርስዎ እርዳታ አስፈልጎናል፡፡

በአጠቃላይ 2.9 ሚሊዮን ብር ያስፈልገናል።ይህን ለማማላች የአካባቢዉ ተወላጆች በኩል ለመሸፈን ስላልተቻለ አቅም ስላነስን መላው ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ከስር በተቀመጠው የባንክ ሒሳብ ቁጥር እንዲያስገባልን መልዕክታችንን እናስተላልፋለን።

ትምህርት ቤቱን ለማገዝ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሒሳብ ቁጥር
1000631143648

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

05 Feb, 17:29


‎የማህበራዊ ሚዳያ አማራጮች በመጠቀም በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ከአከባቢው ተወላጆችና ደጋግ ከሆኑ ሁሉ ሀብት በማሰባሰብ በጉንችሬ ከተማ ለሚኖሩ ለ120 ለሚሆኑ ለአረጋውያንና አቅም ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የማዓጤመ ክፍያና የማዕድ ማጋራት የከተማው አመራሮች በተገኙበት በዛሬው እለት ተከናውኗል።

‎የማህበረሰቡን የመረዳዳትና የአብሮነት እሴት በተግባራቸው አጉልተው በማሳየት እንደ አርአያ ከሚቆጠሩ ወጣቶች መካከል አንዱ የሆነው ተስፋ ነዳ ፣ በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመጠቀም በሀገር ውስጥና ውጭ ከሚኖሩ የአከባቢው ተወላጆች እና ቀና ከሆኑ ሁሉ ሀብት በማሰባሰብ የተቸገሩ ወገኖችን በመርዳት ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ አላማ ማዋል የቻለ ወጣት ነው።

‎የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አ/ቋድር ሂጅራ የማዕድ ማጋራት በተከናወነበት ወቅት እንደገለጹት አቅም ለሌላቸው ለአረጋውያንና ለሌሎችም የማህበረሰብ ክፍሎችን ለመድገፍ በመንግሥት አቅም ብቻ የሚቻል ባለመሆኑ መንግስታዊ ከልሆኑ ደርጅቶች፣ ከከተማው ነጋዴዎችና ከሌሎችም ሰውን ለመረዳት ቅን ከሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ እንዲያደርጉ ትኩረት ስተው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

‎ከነዚህም መካከል አንዱ የሆነው ወጣት ተስፋ ነዳ ከዚህ በፊት ለአረጋውያንና የአቅም ውስንነት ላለባቸው የህበረተሰብ ክፍሎች የማዓጤመ ክፍያና ሌሎችንም ድጋፎች እንዲያገኙ ማድረጋቸውን ተናግረዋል

‎አሁንም ሰዎች በገንዘባቸው ልክ ሳይሆን በህመማቸው ልክ እንዲታከሙ መከፈል ለማይችሉ 120 ለአረጋዊያንና አቅመ ለሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የማዓጤመ አገልግሎት እንዲጠቀሙ መክፈሉን የገለጹት አቶ አ/ቋድር ሂጅራ ወጣት ተስፋ ነዳ እያደረገው ላለው በጎ ተግባር በከተማው አስተዳደር ስም አመስግነዋል።

‎የጉንችሬ ከተማ አስተዳደር ጤና ዩኒት ኃላፊ አቶ ነክር ሙራድ በበኩላቸው በ2016 በጀት አመት 8መቶ 87 በላይ መክፈል ለማይችሉ የማህበረሰብ ክፍሎች መንግስት ወጪው መሸፈኑንና በዘንድሮውም 9 መቶ 11 ለሚሆኑ መከፈሉን ተናግረዋል ።

‎እንዲሁምከተለያዩ መንግስታዊና መንግስታዊ ከልሆኑ ተቋማት ጋር የማዓጤመ ክፍያ መክፈል ለማይችሉ እንዲከፈላቸው እየተሰራ መሆኑንና በተፈለገው መጠን ድጋፎች ከተገኙ የመድኃኒት እጥረት ይቀረፋል ብለዋል አቶ ነክር ሙራድ ።

‎ሰዎች በገንዘባቸው ልክ ሳይሆን በህመማቸው ልክ እንዲታከሙ ባሉት ውስን ቀናት የማዓጤመ ክፍያ ያልከፈሉ የማህበረሰብ ክፍሎች በአስቸኳይ መክፈል እንዳለባቸው መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ።

‎የማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም የተለያዩ የበጎ ተግባር እንቅስቃሴ የሚያደርገው ወጣት ተስፋ ነዳ እንደገለጸው የተቸገሩ ሰዎች መረዳትና ሲደሰቱ ማየት በገንዘብ የማይገኝ የህሊና እርካታ እንደሚሰጠው ገልጾ፣ በችግር ውስጥም ሆኖ የተቸገሩትን ለመረዳት ከፍተኛ ጉጉት እንዳለው ተናግሯል።

‎በሀገር ውስጥና በውጭ ከሚኖሩ ከአከባቢው ተወላጆችና ደጋግ ከሆኑ ሁሉ ሀብት በማሰባሰብ ለ120 ለሚሆኑ ለአረጋውያንና ተጋላጭ የማህበረሰብ የክፍሎች የማዓጤመ ክፍያና የማዕድ ማጋራት ማድረጉን ገልጿል።

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

05 Feb, 17:29


ማህበራዊ ሚዲያ ለበጎ ተግባር በመጠቀም ለአረጋውያንና አቅም ለሌላቸው የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ ድጋፎችን የሚያደረገው ወጣት ተስፋ ነዳ።

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

27 Jan, 13:24


ይህ በፎቶ የምታዩት ልጅ በእኖር ወረዳ ኧሰኸር በሚባል ቀበሌ የተወለደ ሲሆን ስሙ ሙሃጅር አህመድ ይባላል እድሜው 23 ነው። በአሁን ሰአት በደም ካንሰር ተይዞ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ተኝቶ እየታከመ ይገኛል። ቤተሰቡ ምንም የማሳከም አቅም የሌላቸው በመሆኑ የበኩላችሁ እንድትወጡ በፈጣሪ ስም እንማፀናለን። አሳካሚው ወንድሙ አብዱልሰመድ አህመድ

ስልክ ቁጥር 0911786544
የባንክ አካውንት 1000362457468 አብዱልሰመድ አህመድ ሁሴን

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

25 Jan, 18:48


በጌቶ ወረዳ በወንዝሬ ጎረት ቀበሌ ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በአማርድ ቡራት የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት፣ በአካባቢ ተወላጆች ማህበርና በመንግስት የተገነባው የቡራት አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ።

የኢፌድሪ ህብረት ስራ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር የጌታ ወረዳ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ሺሰማ ገብረስላሴ በምረቃው ተገኝተው እንዳሉት ጠንክሮ በመማር ከአካባቢ፣ ከሀገር አልፎ በአለም ደረጃ ተጽዕኖ መፍጠር እንደሚቻል ጠቁመው ለዚህም ትውልዱ በትምህርታቸው ጠንክረው እንዲማሩም አሳስበዋል።

የትምህርት ቤቱ ደረጃ ለማሻሻል የአማርድ የቀድሞ የቡራት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረትና የአካባቢው ተወላጆችና መንግስት ላደረጉት አስተዋጽኦ አመስግነዋል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳደሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ በበኩላቸው ባለፉት አመታት በሀገሪቱ ብሎም በዞኑ መንግስት ለትምህርት ልማት ዘርፍ የተለየ ትኩረት በመስጠት ትምህርት ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ በተሰሩ ስራዎች አመርቂ ውጤቶችን ተመዝግቧል ብለዋል።

በመሆኑም ትምህርት ለዜጎች ለማዳረስ ቢሰራም ደረጃቸውን የጠበቁ ትምህርት ቤቶች፣ ግብአቶችና ሌሎችም አስተዳደራዊ ችግሮችን ተዳምረው በተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር የሚፈለገውን ውጤት ማስመዝገብ አለመቻሉን ገልጸዋል።

በዞኑ ያጋጠመው የተማሪዎች ውጤት ስብራት ችግር ለመፍታት ባለፉት አመታት በንቅናቄ ስራ ማህበረሰቡ፣ ባለሀብቶች፣ ምሁራንና አጋር ድርጅቶችና መንግስት በመተባበር ከ4 መቶ 93 ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት በማሰባሰብ የትምህርት መሰረተ ልማት ማሻሻል ተችሏል ነው ያሉት።

በዞኑ ከደረጃ በታች ከነበሩ ትምህርት ቤቶች መካከል የቡራት 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንዱ እንደነበር አስታውሰው የአማርድ ቡራት የቀድሞ ተማሪዎች ህብረት፣ በአካባቢው ተወላጆች፣ በመንግስት ትብብር መገንባቱን ገልጸዋል።

ማህበሩ የትምህርት ቤቶች መልሶ ግንባታና ግብአት በሟሟላትና በሌሎችም ልማቶች እያደረገው ያለው ድጋፍ አመስግነው በቀጣይም የዞኑ መንግስት የተጀመረው የትምህርት መሰረተ ልማት ማሻሻል ስራ ላይ ድጋፋቸው አጠናክረው እንዲያስቀጥሉም ጠይቀዋል።

የዞኑ መንግስት በትምህርት ልማት ስራ የጀመራቸው ስራዎችን በማጠናከር በቀጣይም ያጋጠመውን የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር ችግሮችን ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራ አስገንዝበዋል።

የጌታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ በህሩ ኸይረዲን የቡራት አጠቃላይ ሁለተኛ ትምህርት ቤት በ2013 ዓ.ም ወደ መሰናዶ ቅድመ እውቅና ቢያገኝም ስታንዳርዳቸው የጠበቁ የመማሪያ ክፍሎች፣ የአስተዳደር ክፍሎች እጥረት፣ የቤተ መጽሀፍትና የቤተ ሙከራ ግንባታዎች እጥረት እንደነበሩበት አንስተዋል።

ይህ ችግር ለመፍታት የአማርድ የቀድሞ የቡራት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረትና የአካባቢው ተወላጆችና መንግስት በመቀናጀት ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የተማሪ የመማሪያ ክፍሎች፣ የማጣቀሻ መጽሀፍቶች፣ የተማሪ መቀመጫ ዴስኮችና ላፕቶፖችን ማሟላት ተችላል ብለዋል።

ይህ ጅምር ስራ በቀጣይም በማጠናከር በትምህርትና በሌሎችም መሰረተ ልማቶች ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳደሪና የትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀብቱ ወልደ ኢየሱስ በወረዳው ቅድመ መደበኛ ጨምሮ ከ1ኛ እስከ12ኛ ክፍል 15 ሺህ 504 ተማሪዎች የሚገኙ ሲሆን የቡራት አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አንዱ ነው።

የአማርድ የቀድሞ የቡራት ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረትና አካባቢው ተወላጆች ማህበር ሰብሳቢ አቶ ዋቢ ታደሰ በ2012 ዓ.ም የተቋቋመው ማህበሩ በትምህርት፣ በጤና በአካባቢ ጥበቃና በመሰረተ ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ ይሰራል ነው ያሉት።

በዚህም በገጠር፣ በከተማ፣ በውጭ ሀገር የሚኖሩ ተወላጆችና መንግስት በመተባበር 4 ደረጃቸውን የጠበቁ የመማሪያ ክፍሎች፣ 12 የመማሪያና የአስተዳደር ህንጻዎችና የቤተመጸሀፍት እድሳት፣ የላይብረሪ፣ የአይሲቲ፣ የላብራቶሪ ቁሳቁሶች፣ የተማሪዎች መግቢያና መውጫ በር ስራ ተሰርቷል ብለዋል።

የአካባቢው ተወላጅ አቶ ገብሩ ምኑታ እንዳሉት የትምህርት ቤቱ ችግር ተቀርፎ ደረጃቸውን የጠበቁ የመማሪያ ክፍሎች ተገንብቶ በመመረቁ መደሰታቸውን ጠቅሰው ይህም የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር በማሻሻሉ ረገድ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በትምህርት ቤቱ አግኝተን ያነጋገራቸው ተማሪዎች እንዳሉት ትምህርት ቤቱ ተገንብቶ በመመረቁ ደስተኛ መሆናቸውን ጠቅሰው በዚህም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ጠንክረው እንደሚሰሩ ጠቁመዋል።

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

21 Jan, 15:43


112000 ብር አሰባስበን ደጋፊ ለሌላቸው 86 አረጋውያን ከነቤተሰባቸው የአመት የመታከምያ ገንዘብ ከፍለናል ‼️ 154 ቤተሰቦች ገና ይጠብቁናል።

በገጠር የሚገኙ ወገኖቻችን በአመት አንዴ ክፍያ እየከፈሉ አመቱን ሙሉ ህመም ባጋጠማቸው ጊዜ ሁሉ የሚታከሙበት የጤና መድህን ስርአት ተዘርግቷል። ነገር ግን ይሄን ክፍያ መክፈልም የማይችሉ ብዙ አረጋውያን አሉ። አምና በዚህ ሰአት በጉንችሬ ከተማ ለሚገኙ 68 አቅመ ደካማ አረጋውያን ና የተለያየ ፅኑ ህመም ያለባቸው ወገኖቻችን አመቱን በሙሉ ሳይሳቀቁ ያለተጨማሪ ወጪ እንዲታከሙ በማሰብ የሚጠበቅባቸውን ክፍያ በፌስቡክ አሰባስበን ከፍለንላቸው አመቱን ሙሉ ሲጠቀሙ ከርመዋል። ዘንድሮ ወደ ሌሎች ቀበሌዎችም ተሻግረን 241 ቤተሰብ ልንደግፍ አመቱን ሙሉ ከሰቀቀን ልናድናቸው ተነስተናል‼️

የቀረን አንድ ሳምንት ብቻ ነው‼️

ሀይማኖት ብሄር ፆታ ሳንለይ የሰበሰብናቸው አቅም የሌላቸው ወገኖቻችን ከጤና ወጪ ስጋት ለአንድ አመት ነፃ እንዲሆነ መቶ ብር በማዋጣት እንድታግዙን እንጠይቃለን🙏😍

ፅገሬዳ ሰቦቃ ና ተስፋ ነዳ
1000620986864
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

21 Jan, 15:17


ጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ፉቻሬ-44 ቀበሌ ቅዳሜ ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በተፈጠረ የእሳት አደጋ 11 ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ወድመዋል!

ተጎጂዎችን ለማቋቋም  በሀገር ሽማግሌዎችና በወረዳው አስተዳደር ትብብር የእርዳታ አካውንት ተከፍቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
አንድ ሺ 673072 አራት ስልሳ አምስት

ከዚህ አካውንት ውጪ የሚደረጉ የእርዳታ ማሰባሰቦች በሙሉ ህጋዊ አለመሆናቸውን እንገልፃለን።

የእርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ
ከወረዳው አስተዳደር ጋር በመተባበር!

EMAT GURAGE MEDIA

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

18 Jan, 20:21


#ጥንቃቄ

በጉራጌ ዞን ጌታ ወረዳ ፉቻሬ-44 ቀበሌ ዛሬ ከሰዓት ምክንያቱ ባልታወቀ ሁኔታ በተፈጠረ የእሳት አደጋ 11 ቤቶች ሙሉ ለሙሉ መውደማቸው ተገልጿል።

ከወረዳው ባገኘነው መረጃ መሰረት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብዙ ቦታዎች በቤት ቃጠሎ በርካታ ንብረት እየወደመ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በጋው በጣም እየጠነከረና አየሩ ነፋሻማ ስለሆነ ማህበረሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ ይገባልም ተብሏል።

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

09 Jan, 13:26


እናትን ለሚወድ ሁሉ ይኼን አድርሱልኝ

በገጠር የሚገኙ ወገኖቻችን በአመት አንዴ ክፍያ እየከፈሉ አመቱን ሙሉ ህመም ባጋጠማቸው ጊዜ ሁሉ የሚታከሙበት የጤና መድህን ስርአት ተዘርግቷል። ነገር ግን ይሄን ክፍያ መክፈልም የማይችሉ ብዙ አረጋውያን አሉ።

አምና በዚህ ሰአት በጉንችሬ ከተማ ለሚገኙ  68 አቅመ ደካማ አረጋውያን ና የተለያየ ፅኑ ህመም ያለባቸው ወገኖቻችን አመቱን በሙሉ ሳይሳቀቁ ያለተጨማሪ ወጪ እንዲታከሙ በማሰብ የሚጠበቅባቸውን ክፍያ በፌስቡክ አሰባስበን ከፍለንላቸው አመቱን ሙሉ ሲጠቀሙ ከርመዋል።

እንደ ተስፋ ቲቪ ባለፈው አመት በመቶ ብር ቻሌንጃችን  ለጤና መድህን ብቻ ሳይሆን ወልቂጤ ላይ ለሁለት መቶ አረጋውያን በሁለት ዙር የምገባ ፕሮግራም አድርገናል። የአረፋን በአልም በክትፎ አክብረንላቸዋል። 

በዘንድሮው የመስቀል በአልም በጉንችሬ ሰንጋ ጥለን ለእናቶቻችን ቅርጫ አከፋፍለናል።

በአንድ ቀበሌ ተወስኖ የነበረው የጤና መድህን ስራችን ሰፍቶ ዘንድሮ በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች ተደራሽ የሆነ ስራ እንሰራለን። በዚህም ለ 241 ቤተሰብ ሆነውብናል። በዚህም በከተማ አስተዳደሩ በተፃፈልን ደብዳቤ መሠረት ለአንድ ቤተሰብ 1300 ብር ከፍለን የሁሉንም ለማጠናቀቅ 312000 ብር ስለሚያስፈልገንና የቀረንም አስር ቀን በመሆኑ በፌስቡክ ስንሰራው የቆየነውን ስራ ወደ ቲከሰቶክም አምጥተነዋል።

እነሆ ዘንድሮሞ የ240 ቤተሰብ የአመት የጤና መድህን ክፍያ እንከፍላለን። በአካልም ጥር 12 ተገኝተን ሰርተፍኬታቸውን ሰጥተን እንመረቃለን።

ሀይማኖት ብሄር ፆታ ሳንለይ የሰበሰብናቸው አቅም የሌላቸው ወገኖቻችን ከጤና ወጪ ስጋት ለአንድ አመት ነፃ እንዲሆነ መቶ ብር  በማዋጣት እንድታግዙን እንጠይቃለን🙏😍

ፅገሬዳ ሰቦቃ ና ተስፋ ነዳ
1000620986864
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

09 Jan, 13:01


https://youtu.be/PAN6zNfPzFc

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

09 Jan, 12:59


በወልቂጤ ከተማ በጉራጊኛ ቋንቋ ና ኪነ ጉራጌ ላይ የተዘጋጀ የኪነጥበብ መድረክ እየተካሄደ ነው።

ለዝርዝሩ ይጠብቁን🙏

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

05 Jan, 17:46


እኝህን እናት ጨምሮ 240 ቤተሰቦች አመቱን በሙሉ ወደ ጤና ጣብያ መሄድ የሚችሉት እኛ ተጋግዘን የአመት የጤና መድህን ክፍያቸውን መክፈል ስንችል ብቻ ነው። አመቱን በሙሉ ፈጣሪን እየለመኑ እኛንም እየመረቁ.. "ብታመም ማን ያሣክመኛል "ከሚል ስጋት ወጥተው እንዲከርሙ እገዛችሁን እጠይቃለሁ።

አምና ለ 68 ቤተሰብ ይሄን አሳክተናል ዘንድሮስ

ገና አስራ ሁለት ቤተሰብ ብቻ ነው የሸፈንነው 🙏 እንበርታ🙏

ሀይማኖት ብሄር ፆታ ሳንለይ የሰበሰብናቸው አቅም የሌላቸው ወገኖቻችን ከጤና ወጪ ስጋት ለአንድ አመት ነፃ እንዲሆነ መቶ ብር በማዋጣት እንድታግዙን እንጠይቃለን🙏😍

የአንድ ቤተሰብ ክፍያ 1300 ብር
ስም ዝርዝር የተላከልን አባወራ ብዛት 241

በቻሌንጁ ለማሣተፍ የተለመደውን የበጎ አድራጎት አካውንት
ይጠቀሙ🙏

ፅገሬዳ ሰቦቃ ና ተስፋ ነዳ
1000620986864
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

ለእናቶቻችን ጤና ከመቶ ብር ጀምሮ ተሳትፋችሁ ኮሜንት ላይ አስቀምጡልኝ። ብዙ ሰው እንዲያየው ኮሜንት ላይክ ማረግ አትርሱ🙏

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

05 Jan, 16:19


https://youtu.be/8BMZWmXkGgc

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

03 Jan, 15:21


የገጠር ትምህርት ቤቶች ያሉበትን ሁኔታ እያየን ቀርፀን በዶክመንታሪ ለብዙ ሺ ህዝብ እያሳየን ቆይተናል።

በእኖር ወረዳና በእኖር ኤነር መገር ወረዳ ያልቀረፅናቸው ብርቱ ድጋፍ የሚሹ ከ25 በላይ ትምህርት ቤቶች አሉ።

የእስካሁኑ ስራችን በ Tesfa Tv ወጪ የተሰሩ በመሆናቸው ከዚህ በኋላ ለመቀጠል የተመልካች ድጋፍ ያስፈልገናል።

በአቅማችሁ ለመደገፍ ፍቃደኛ የሆናችሁ ኮሜንት ላይ "እኔ ፈቃደኛ ነኝ " በሉን 🙏

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

03 Jan, 12:00


ታላቅ አላማ አብረን እናሣካ🙏 እባካችሁ ሼር ማረግ አትርሱ🙏

አምና በዚህ ሰአት በጉንችሬ ከተማ የሚገኙ 68 አቅመ ደካማ አረጋውያን ና የተለያየ ፅኑ ህመም ያለባቸው ወገኖቻችን አመቱን በሙሉ ሳይሳቀቁ ያለተጨማሪ ወጪ እንዲታከሙ በማሰብ የሚጠበቅባቸውን ክፍያ እዚሁ አሰባስበን ከፍለንላቸው አመቱን ሙሉ ሲጠቀሙ ከርመዋል። ባለፈው አመት በመቶ ብር ቻሌንጃችን ለጤና መድህን ብቻ ሳይሆን ወልቂጤ ላይ ለሁለት መቶ አረጋውያን በሁለት ዙር የምገባ ፕሮግራም አድርገናል። የአረፋን በአልም በክትፎ አክብረንላቸዋል። በዘንድሮው የመስቀል በአልም በጉንችሬ ሰንጋ ጥለን ለእናቶቻችን ቅርጫ አከፋፍለናል።

በአንድ ቀበሌ ተወስኖ የነበረው የጤና መድህን ስራችን ሰፍቶ ዘንድሮ በከተማ አስተዳደሩ ስር በሚገኙ በሁሉም ቀበሌዎች ተደራሽ የሆነ ስራ እንሰራለን። በዚህም ለ 241 ቤተሰብ የአመት የጤና መድህን ክፍያ እንከፍላለን። በአካልም ተገኝተን ሰርተፍኬታቸውን ሰጥተን እንመረቃለን።

ሀይማኖት ብሄር ፆታ ሳንለይ የሰበሰብናቸው አቅም የሌላቸው ወገኖቻችን ከጤና ወጪ ስጋት ለአንድ አመት ነፃ እንዲሆነ መቶ ብር በማዋጣት እንድታግዙን እንጠይቃለን🙏😍

የአንድ ቤተሰብ ክፍያ 1300 ብር
ስም ዝርዝር የተላከልን አባወራ ብዛት 241

በቻሌንጁ ለማሣተፍ የተለመደውን የበጎ አድራጎት አካውንት
ይጠቀሙ🙏

ፅገሬዳ ሰቦቃ ና ተስፋ ነዳ
1000620986864
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

የከተማ አስተዳደሩ ህጋዊ ደብዳቤ ፣ የአምና ማስታወሻዎች በፖስቱ ላይ ተካተዋል🙏😍

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

02 Jan, 10:44


https://youtu.be/9R4xz0KYgh8

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

01 Jan, 12:12


https://youtu.be/ZPlL7_A9T40

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

26 Dec, 13:49


የጉራጌ ህፃናት መማር የለባቸውም

የገጠር ትምህርት ቤቶቻችንን ... የገጠር ሰፈሮቻችንን ... ያሉበት ሁኔታ አይተን ለእናንተም አሳይተናችኋል!

ባለፉት ወራት ከ 15 በላይ ትምህርት ቤቶችና ከ ሰባት በላይ አነስተኛ ከተሞች ያሉበትን ሁኔታ በዶክመንታሪ አቅርበናል!

ቪድዮዎቹን ሚሊየኖች ተመልክተዋቸዋል! የቀድሞ ተማሪዎች እየተሠባሠቡ ትምህርት ቤቶቻቸውን ለመደገፍ እንቅስቃሴ ጀምረዋል! ቪድዮዎቹ በሁሉም ሶሻል ሚዲያዎች በነፃ እንዲሰራጩ ስናደርግ አላማችንም ይኸው ነበረ! ለማደስና ለተማሪዎች ደብተርና መፅሀፍ ለማሟላት የተደራጀ እንቅስቃሴ የሚጀምሩ ትምህርት ቤቶችንም መልሰን ለእናንተው እናቀርባለን።

ከችግሩ ስፋት አንፃር የሰራነው ጥቂት ነው። ገና ብዙ ትምህርት ቤቶችንና ከተማዎችን ማነቃቃት እናቅዳለን።  ነገር ግን የእስካሁኑን ስራ  የሰራነው በአብዛኛው በራሳችን ወጪ በመሆኑ ከዚህ በላይ ለመቀጠል የእናንተ ድጋፍ አስፈልጎናል።

በቀጣይ ሳምንት በሶስተኛ ዙር ወደ እኖር ፣ ጌቶ ና ጉመር ወረዳዎች ተጉዘን ትውልዱ እንዴት እየተማረ እንደሆነ እናሣያችኋለን ። ይህን ማድረግ የምንችለው ግን በመቶ ብር ቻሌንጅ ሁላችሁም ስትሳተፉ ነው። ስለሆነም የአላማችን ደጋፊ መሆናችሁን በቀጣይ በተገለፁ አካውንቶች መቶ ብር በማገዝ አጋርነታችሁን አሳዩን።

ንግድ ባንክ - 1000654868097
አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

ቴሌ ብር

0924410897

እናመሠግናለን🙏

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

23 Dec, 16:27


https://youtu.be/5CkXBLZAVDY

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

21 Dec, 18:26


ይሄን ጩጬ የዛሬ አራት አመት ጉብሬ ሄጄ ኢንተርቫው ሳደርገው ትልቅ ለውጥ ፈጣሪ እንደሚሆን ጥርጥር አልነበረኝም። ካሰብኩት በላይም አድርጎ ስላሳየኝ ደስ ብሎኛል። አሁን ደግሞ ብርቱ ውድድር ላይ ነውና ድምፃችንን ይፈልጋል።

በአንቴክስ ኢትዮጵያ ሸላሚነት በተዘጋጀው BIWs Prize የሽልማት ፕሮግራም በኢኮኖሚ ዘርፍ ተወዳዳሪ ለሆነው ኢዙ የ10 ሚሊዮን ብር አሸናፊ የሚያደርገው የመጨረሻና ወሳኝ ድምጽ በእርሶ እጅ ነው። BIW02 በማለት ወደ 9355 አጭር ቁጥር ድምጽ ይስጡ።

ስክሪን ሻት ኮሜንት ላይ አስቀምጡልኝ🙏

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

17 Dec, 12:28


ትኩረት ካላገኙ ትምህርት ቤቶች መሀል አንደኛው ‼️

ቪድዮ ዩቱዩብ ላይ ተለቋል‼️

https://youtu.be/Gk904xN6q_0?si=urPb2E2njizfRABfRABf

TESFA TV

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

17 Dec, 12:28


https://youtu.be/Gk904xN6q_0?si=urPb2E2njizfRABf

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

20 Nov, 14:51


https://youtu.be/Djge0DyISVo

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

13 Nov, 11:15


ደረሰ ደረሰ ‼️ ለዛውም ለፆም መያዣ ‼️

ተፈጥሮዋዊ ቦታዎችን ጎብኝተን የጉራጌን ባህላዊ ምግብ በልተን ልንመጣ ነው‼️

🚌 ጉዞ ወደ ናይካም ፏፏቴ ና አጋሬ መንደር 🚌

🍃🍃 ጊቤ ፓርክ ጉራጌ 🍃🍃

በቅርቡ በአርቲስቶችና ጋዜጠኞች አስጎብኝተነው ዝናን ያተረፈው የአጋሬ መንደር አሁን ለሁላችሁም ዝግጁ ሆኗል‼️

📅 መነሻ ቅዳሜ ህዳር 14 , 2017
📅 መመለሻ ህዳር 15 ,2017

💵 የጉዞ ሂሳብ 4999 ብር

የጉዞ ሂሳብ የሚያካትተው

🚍 ትራንስፖርት ዘመናዊ አውቶብስ

🥗 ምግብ ጥሬ ስጋ ፣ ክትፎ ፣ ብራፕራት ፣ ቡላ ገንፎ

💧የታሸገ ውሀ, ቡና, አስጎብኚ

🔥 የምሽት ካምፋየር 🔥 ና ፎቶግራፍ 📷

ሁሉንም በ ሙሉ ፓኬጅ 4999 ብር

ለቤተሰብ - ለፍቅረኞች - ለጓደኛማቾች ለሁሉም የተመቸ 🏕️

ውብ የተፈጥሮ እይታ እያዩ መዝናናት ለሚወዱ ም Adventure ለሚመቻቸውም የሚሆኑ አማራጮች ያሉት!

ለመመዝገብ 0924410897 ላይ ቴክስት ይላኩልን ። ክፍያ ሲፈፅሙ ወንበር ይያዝሎታል።

ጉዞ ጉራጌ - TESFA TV

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

10 Nov, 16:05


🚌 ጉዞ ወደ ናይካም ፏፏቴ ና አጋሬ መንደር 🚌

🍃🍃 ጊቤ ፓርክ ጉራጌ 🍃🍃

°°°°

በቅርቡ በአርቲስቶችና ጋዜጠኞች አስጎብኝተነው ዝናን ያተረፈው የአጋሬ መንደር አሁን ለሁላችሁም ዝግጁ ሆኗል‼️

📅 መነሻ ቅዳሜ ህዳር 14 , 2017
📅 መመለሻ ህዳር 15 ,2017

💵 የጉዞ ሂሳብ 6000 ብር

የጉዞ ሂሳብ የሚያካትተው

🚍 ትራንስፖርት ዘመናዊ አውቶብስ

🥗 ምግብ ጥሬ ስጋ ፣ ክትፎ ፣ ብራፕራት ፣ ቡላ ገንፎ

💧የታሸገ ውሀ, ቡና, አስጎብኚ

🔥 የምሽት ካምፋየር 🔥 ና ፎቶግራፍ 📷

ሁሉንም በ ሙሉ ፓኬጅ 6000 ብር

ለቤተሰብ - ለፍቅረኞች - ለጓደኛማቾች ለሁሉም የተመቸ 🏕️

ውብ የተፈጥሮ እይታ እያዩ መዝናናት ለሚወዱ ም Adventure ለሚመቻቸውም የሚሆኑ አማራጮች ያሉት!

ለመመዝገብ 0924410897 ላይ ቴክስት ይላኩልን ። ክፍያ ሲፈፅሙ ወንበር ይያዝሎታል።

ጉዞ ጉራጌ - TESFA TV

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

06 Nov, 15:11


https://youtu.be/0FaViGT0gVI

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

06 Nov, 15:10


ገና ሳይጠናቀቅ 8 ሚሊየን ብር የፈጀው የጉራጌ ጎጆ ቤት‼️

የጉራጌን የቱሪዝም አብዮት ካፈነዳው " ጉዞ ጉራጌ 3" መልስ ሌላኛው የቱሪዝም ሀብታችን የሆነው የጉራጌ ጎጆ ቤት አሰራር ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ ልናይ ወደ እዣ ተጓዝን። ከጉብሬ ተነስተን ወልቂጤ ዩንቨርስቲን ካለፍን በኋላ አስፋልቱን በመተው ወደ ፒስታው ገባን። የተንጣለለውን የእዣ ለምለም ምድር እያየን የበረሳ ውርኼ ቀበሌ ደርሰናል።

ወሰኑን የዋቤ ወንዝን ያደረገው ቀበሌው ከወንዙ ማዶ ከቃጥባሬ ጋር ይተያያል። በዚህ አስቸጋሪ መንገድ አልፈው የተማሩትና አሁን በአሜሪካን ሀገር የሚገኙት አቶ አካሉ ደንድርና ወንድሞቻቸው እንደ አብዛኛው ጉራጌ ቀዬአቸውን ትተው ቢወጡም ልባቸው ግን እዚሁ ነውና እንግዳ ቢመጣ የማያፍርበት ዘመድ የሚሰባሰብበት ግዙፍ ጎጆ ገነቡ። ጎጆው ስምንት ሚሊየን ብር እንደፈጀ ሰምተናል። ይህን ሁሉ ሀብት በቀዬአቸው ማፍሰሳቸው ለብዙዎች ትምህርት ሊሆን የሚገባው ነው።

ከመጓጓታችን የተነሣ "ኧረ ገና ቤቱ አላለቀም ባህላዊ ወንበሮችና ቁሳቁሶች አልገቡም ለምርቃቱ ትመጣላችሁ " ቢሉንም ከመቅረፅ አልተመለስንም።

ይሄ ነው ጉራጌ ‼️ ይሄ ነው ባህልን መጠበቅ‼️

ተስፋ ቲቪ ከ ጉራጌ እዣ በረሳ ውርኼ

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

03 Nov, 13:25


የጉራጌ አካባቢ የተፈጥሮ ሀብት፤ ገና ያልተመነዘረና ያልተነካ፥ ለህዝቡ ከፈጣሪ የተቸረ ገደብ የለሽ፥ ሀብት ነው።

ለማህበረሰቡ ሲሳይና በረከት፤ የሆነው ይህ የተፈጥሮ ሀብት፤ በ"ጉዞ ጉራጌ" 3 ታዳሚዎች ዘንድ፥ አሳማኝነቱ እየተረጋገጠ፥ ቁጭት ፈጥሮ፤ የወደፊት ተስፋ ላይ የራሱን አስተዋፅዖ በማበርከትና ተነሳሽነት እንዲጎላ በማድረግ፥ ጉብኝቱ እየቀጠለ ይገኛል።

በ TESFA TV "ተስፋ ቲቪ" የተሰናዳው ይህ "ጉዞ ጉራጌ" 3 የተሰኘው መርሃግብር፤ ጋዜጠኞች፣ ሚዲያዎች፣ የቱሪዝም ጋዜጠኞች፣ ካሜራማኖችና ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ይዞ፤ ወደ ጉራጌ አካባቢ፥ ዛሬ ማለትም በዕለተ ቅዳሜ፥ በ23-02-2017 ዓ.ም. ከትሟል።

በዚህኛው "ጉዞ ጉራጌ" 3 የመርሃግብሩ ተመራጭ ቦታ፤ "ጊቤ ሸለቆ ብሔራዊ ፓርክ" ሲሆን፤ በዕለቱ እንግዶች እና ጥሪ በተደረገላቸው ባለድርሻ አካላት አማካኝነት፤ ቀኑን ሲጎበኝ ውሏል! አመሻሹም በ"ጉዞ ጉራጌ" 3 ጎብኚዎች እየደመቀ ይገኛል።

የጉራጌ ህዝብ ያሉት ያልተመነዘሩ ሀብቶች፤ በዚህ መርሃግብር እየተዳሰሰ ይገኛል። ባህላዊ ምግቦች ጨምሮ፤ የጉራጌ ባህል፣ ወግ፣ ስርዓትና ማንነት፥ በተግባር ለጎብኚዎች እንደ መፅሐፍ እየተገለጠ ሲንፀባረቅም ተስተውሏል።

በአጠቃላይ፤ በወሬ ሳይሆን በተግባር የሚያምን ትውልድ፣ የሚሰራና የሚያሰራ ማህበረሰብ፣ ለአካባቢው ተቆርቋሪ የሆነ አምራች ወጣት፣ ለመልካም አስተዳደር ትግበራና ለዘላቂ ልማት፥ የራሱን ድርሻ የሚወጣ አመራርና ባለድርሻ አካል እንዲሁም ተቆርቋሪ ባለሀብት፤ የጉራጌ ህዝብ ይሻል። የተግባር ሰው ይፈልጋል።

የዚህ ጉዞ መሳካት ላይ፤ የራሳችሁን ጉልህ አስተዋፅዖ የተወጣችሁ ሁሉ፤ እንኳን ደስ አላችሁ 🙏 እናንተ የስኬታማነት መሰላሎች ናችሁ። የ"ጉዞ ጉራጌ" 3 ስኬት፥ የእናንተም ስኬት ነው። በይመለከተኛል ዕሳቤ፤ እናንተ ከእኛ ጋር ነበራችሁ፤ እኛም ሁሌም ከእናንተ ጎን አለን ለማለት እንወዳለን።

የጉብኝቱ አጠቃላይ ይዘት፤ በቀጣይ ቀናቶች እናደርሳለን.....

ለማንኛውም "ጉዞ ጉራጌ" 3 ከስኬት ጋር እየቀጠለ፤ ድባቡም እያማረ ይገኛል. . . . .!!

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

01 Nov, 17:00


የጉራጌ ቀዬ አመቱን ሙሉ ደምቆ ... ኢንቨስትመንትና ቱሪዝም ተስፋፍቶ ... ጉራጌው ብቻ ሳይሆን መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ተጠቃሚ እንዲሆን ምኞታችን ነው።

ድህነትና የልማት እጦት በማዘን ና በቁጭት ብቻ እንደማይፈታ እነሠምናለንና ለመፍትሄው እየተጋን ነው። የቱሪዝም መስህቦችን መፈለግ ፈልጎም ማስተዋወቅ ቱሪስቶችን መጥራት ለብዙዎች የስራ እድል መፍጠር ላይ ወጥረን እየሠራን ነው። ገና ከጅምሩ ውጤታችን ፍሬ አፍርቶ ቪድዮዎቻችን በመቶ ሺዎች እየታዩ ነው። ገና ሚሊየኖችን እንደርሳለን።

ነገና ከነገ ወዲያ በጊቤ ፓርክ የቱሪዝም ፌስቲቫል እናካሂዳለን። የሚዲያ ና የቱሪዝም ባለሙያዎች በእንግድነት ይገኛሉ። የዚህን ፕሮግራም ውጤትም ከነገ ጀምሮ በጋራ እናየዋለን።

ለዚህ ፕሮግራም እገዛ ስንጠይቅ ከሜየት አልፈው ለተግባር የፈጠኑት ጥቂቶች ቢሆን የጥቂቶች ወኔ እኛን አበርትቶናል። ከሚጠበቅብን ወጪ ገና የሠበሠብነው ግማሹን ነው ። ከዛም ውስጥ ግማሹን የሸፈኑልን ሶስት ሰዎች ጉራጌ ያልሆኑ ግን የጉራጌ ልማት ውጤቱ ለሀገር ነው ብለው የሚያምኑ ናቸው። ደስ አይልም🤔❤️

የጉራጌ ዞን አስተዳደር ፣ የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር ፣ ወልቂጤ ዩንቨርስቲ ፣ የጊቤ ፓርክ አስተዳደር ና የእኖር ወረዳ አስተዳደር የቻሉትን እየደገፉን ነው። የሁሉንም ድጋፍ ጠቅሰን እውቅና እንሰጣለን🙏

ለመልካም ብለን በተነሳንበት ጉዞ በእዳ እንዳንወድቅ ከመቶ ብር ጀምሮ በማዋጣት አለንላችሁ በሉን። መልካም መንገድም ተመኙልን🙏❤️

ንግድ ባንክ - 1000654868097

አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

TEAM GUZO GURAGE

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

31 Oct, 19:11


የጉራጌን የቱሪዝም ዘርፍ የሚያነቃቃው ትልቁ የሚዲያ ፌስቲቫል ሊደረግ አንድ ቀን ብቻ ቀርቷል‼️

ያገኘነው ድጋፍ ግን ግማሽም አልደረሰም

አሁንም ድጋፋችሁን እየጠበቅን ነው

እየተቆለጳጰሱ ብቻ፤ ተግባር ከራቀን፥ እንደ ማህበረሰብ እንከሽፋለን..

በዓመት ሁለት ወቅቶች፤ የጉራጌ አካባቢ ደብቆ፣ ፈክቶና አጉምዥቶ እንዲሁም ተናፋቂ በሆነ አኳኋን የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን አስተናግዶ፤ ያልፋል።

በእነዚህ ወቅቶች የሚስተዋሉ የአንድነትና የመተሳሰር እውነታዎች፤ ለሌሎች ዓርአያነት ያለው ተግባር በመሆኑ፥ ሁሌም ይወደሳል። ይቆለጳጰሳል።

ታድያ ለምን ሁሉም ወቅቶች ላይ፤ የጉራጌ አካባቢ ፈክቶ፥ እንዲያንፀባርቅ ማድረግ ተሳነን?

በማህበረሰቡ ርብርብና በበጎ ፍቃደኝነት ላይ በተመሠረተው በዚህ የማህበረሰብ የውዴታ ግዴታ በሆነው ተግባር ላይ፤ ከ100 ብር ጀምሮ፤ የራስ አስተዋፅዖ በማድረግም፥ አሻራዎትን በማሳረፍ "ጉዞ ጉራጌ" 3 የተሰኘው መርሃግብር እንዲሳካ እናድርግ። ማህበረሰባዊ ሀላፊነታችንን እንወጣ።

ለማህበረሰብ አገልግሎት ድጋፍ 👎

ንግድ ባንክ - 1000654868097

አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

29 Oct, 17:45


እየተቆለጳጰሱ ብቻ፤ ተግባር ከራቀን፥ እንደ ማህበረሰብ እንከሽፋለን..

በዓመት ሁለት ወቅቶች፤ የጉራጌ አካባቢ ደብቆ፣ ፈክቶና አጉምዥቶ እንዲሁም ተናፋቂ በሆነ አኳኋን የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎችን አስተናግዶ፤ ያልፋል።

በእነዚህ ወቅቶች የሚስተዋሉ የአንድነትና የመተሳሰር እውነታዎች፤ ለሌሎች ዓርአያነት ያለው ተግባር በመሆኑ፥ ሁሌም ይወደሳል። ይቆለጳጰሳል።

ታድያ ለምን ሁሉም ወቅቶች ላይ፤ የጉራጌ አካባቢ ፈክቶ፥ እንዲያንፀባርቅ ማድረግ ተሳነን?

የተፈጥሮ ሀብቶቻችን፤ እጅግ ያማሩና ሀገሪቷ ካሏት ሀብቶች ውስጥ በቁጥር ሊጠቀሱ የሚችሉ ናቸው። እነዚህን የተፈጥሮ ሀብቶቻችን፤ ለወጣቶች የስራ ዕድል፣ ለማህበረሰቡ የተፋጠነ ልማት፣ ለዘላቂ የሀብት ምንጭ፣ ለማህበረሰቡም ሆነ፥ ለመንግስት የገቢ ምንጭ እና ለህዝብ ለህዝብ ትስስር አስተዋፅዖው ከፍተኛ ነው።

ታድያ እንዴት ነው መጠቀም ያለብን? ስር ነቀል ለውጥ እንደ ማህበረሰብ በማምጣት ነው። እሱም፤ ሚዲያዎች፣ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች፣ አንጋፋ ጋዜጠኞች፣ ኢንቬስተሮችና አስጎብኚ ድርጅቶች፤ ወደ ቦታው በመውሰድ፥ አስደማሚና ተወዳጅ የሆኑትን የጉራጌ የተፈጥሮ ሀብቶችን እንደ መነሻ አስጎብኝቶ፤ ዘመን ባፈራቸው በምስሎች፣ በተንቀሳቃሽ ምስሎችና በዘጋቢ ፊልሞች፤ ለሀገራችንና ለዓለም ህዝብ በማስመልከት፤ ቁጭትና ግንዛቤ እንዲፈጠር ማድረግ ነው።

ይህ ተግባር እንዴት ይሳካል?

ይህ ተግባር ለማሳካት፤ ጥቅምት 23 እና 24 "ጉዞ ጉራጌ" 3 የተሰኘ ፕሮግራም ተይዟል። ሁሉም ተጓዦችና ለጉዞው የሚያስፈልጉ ነገሮች ተከናውነዋል።

በማህበረሰቡ ርብርብና በበጎ ፍቃደኝነት ላይ በተመሠረተው በዚህ የማህበረሰብ የውዴታ ግዴታ በሆነው ተግባር ላይ፤ ከ100 ብር ጀምሮ፤ የራስ አስተዋፅዖ በማድረግም፥ አሻራዎትን በማሳረፍ "ጉዞ ጉራጌ" 3 የተሰኘው መርሃግብር እንዲሳካ እናድርግ። ማህበረሰባዊ ሀላፊነታችንን እንወጣ።

ከብሽሽቅ፣ ከመናናቅ፣ ከመሰዳደብና ከክፉ ተግባራት በፀዳ መንፈስ፤ በማህበረሰብ አገልግሎት አንድነታችንን በማሳየት፥ ለሌሎችም አርዓያ የምንሆንበትን ተግባር ዕውን እናድርግ።

ለማህበረሰብ አገልግሎት ድጋፍ 👎

ንግድ ባንክ - 1000654868097

አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

28 Oct, 20:09


https://vm.tiktok.com/ZMh9cJbbf/

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

27 Oct, 21:29


https://vm.tiktok.com/ZMh9BW1Ak/

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

25 Oct, 14:58


https://youtu.be/zXQ99qVgmvs

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

21 Oct, 17:16


በአዲስ አበባ መርካቶ ሸማ ተራ የእሳት አደጋ ተከስቷል።

በአዲስ አበባ አዲስ ክ/ከተማ መርካቶ በተለምዶ ሸማ ተራ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር እየተሰራ መሆኑን የከተማዋ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ እንዳሉት÷እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል የእሳት የአደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎችና ባለሞያዎች በስፍራው ተሰማርተዋል፡፡

የእሳት አደጋውን መንስዔና ያደረሰውን ጉዳት ምርመራ ከተጣራ በኋላ እንደሚያሳውቁም ባለሞያው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ
fbc

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

21 Oct, 13:31


ጉዞ ጉራጌ ብለን ስንነሣ ቀድሞ ሞራል የሰጠን ጋሽ Kassa Yimmer ነው። ነሀሴና መስከረም ባደረግናቸው ሁለት ጉዞዎች አስር አስር ሺ ብር ስፖንሰር አርጎናል። አሁንም የኪነጥበብ ባለሙያዎችን ይዘን በመሄድ መነቃቃት ለመፍጠር ስናቅድ በርቱ ብሎን አስር ሺ ብር አግዞናል። እኛም የጉራጌ ልብስ የምንሸልመው ይሆናል🙏

ጋሽ ካሳ አላማችን ለአንድ ብሄር ብቻ አለመሆኑን ተረድቶ ቱሪዝሙ ብዙ ወጣቶች የስራ እድል ቢያገኙ ጥቅሙ ለሀገር ነው ብሎ ከጎናችን ሲቆም አብዛኛው ጉራጌ ግን ባላየ እያለፈን ነው። ጉዞው መደረጉ የማይቀር ና የተፈለገውን ዋጋ ከፍለን የምናሣካው ቢሆንም ዝምታው ግን ያስከፋል።

ይሄን ሁሉ ጮኸን የጋሼን አስር ሺ ጨምሮ ማሠባሠብ የቻልነው 41800 ብር ነው ሲባል መቼም ያሣፍራል።

እስቲ ኮሜንት ላይ አለን በሉ 👏

ንግድ ባንክ - 1000654868097

አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

20 Oct, 12:19


https://youtu.be/HrB3hSzx1jA

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

17 Oct, 18:37


https://vm.tiktok.com/ZMhPfdAsf/

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

17 Oct, 12:39


የጉራጌን ቱሪዝም የማነቃቃት አላማ ያለው "ጉዞ ጉራጌ 3 " በደማቅ ሁኔታ ሊካሄድ አስራ አምስት ቀናት ቀርተውታል። ይህ ጉዞ ከእስከአሁኑ በተለየ መልኩ ሙሉ ለሙሉ የክብር እንግዶችን ብቻ በመያዝ ወደ ጊቤ ፓርክና አካባቢው የሚደረግ ጉብኝት ና ካምፒንግ ነው።

አዳዲስ ነገሮች እንሞክራለን ካምፒንግ አርጎ በደን መሀል ክትፎ እንበላለን። ክትፎ ጫካ ልትገባ ነው😂 ከተፈጥሮ ሀብት አልፈንም የጉራጌ ህፃናት እየተማሩባቸው ያሉ ትምህርት ቤቶችን ና እናቶች ቀድተው የሚጠጧቸውን ወንዞች እናያለን። የጉራጌ ሁለት መልኮች 🤔

" ለዛ ቀን ያድርሰን እንጂ እንመጣለን " ካሉን መሀል ጥቂቱን ዘርዝሬላችሁ የቀሩትን ከባድ እንግዶች ደግሞ ቀጥዬ እመጣበታለሁ።

1 ሄኖክ ስዩም - የቱሪዝም ጋዜጠኛና ደራሲ

2 ተስፋዬ ማሞ - ደራሲና የማስታወቂያ ባለሙያ

3 የሸዋ ማስረሻ - ጋዜጠኛና የሚዲያ አዋርድ አሸናፊ

4 አዳነ አረጋ - ጋዜጠኛና የሚዲያ አዋርድ አዘጋጅ

5 መሠረት በዙ - ጋዜጠኛና ዩቱዩበር

6 ሰያ ኢትዮጵያ - አስጎብኚና ጋዜጠኛ

7 Elatrik (በግሩፕ) - ቲክቶከሮች

8 በረከት ግዛቸው - ተዋናይና የጉማ አዋርድ እጩ

9 ተስፋአብ ተሾመ - ደራሲ

10 ህሊና ተክሌ - ጋዜጠኛና የሴቶች የሚታጠብ ሞዴስ አምራች

11 ሰለሞን ሳህለ - ገጣሚ

ሌሎች ታዋቂ ድምፃውያን ፣ በጎ አድራጊዎች ፣ ኢኮኖሚስቶች ናባለሀብቶች ጥሪ ቀርቦላቸዋል ። በጉዞ ደስተኛነታቸውን ገልፀው ፕሮግራማችንን እንመልከት ብለዋል ። ሲወስኑ አሳውቃችኋለሁ።

አላማችን ያስደሰታችሁ ድርጅቶች ይህን ታላቅ ጉዞ ስፖንሰር አድርጋችሁ ድርጅታችሁን አስተዋውቁ።

ጉዞው እንዲሳካ ከመቶ ብር ጀምሮ ለመደገፍ የምትፈልጉ የሀገራችን ልጆች ከታች ያለውን የጉዞ ጉራጌ አካውንት ተጠቀሙ።

ንግድ ባንክ - 1000654868097

አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

Emat Gurage Media

EMAT GURAGE MEDIA እማት ጉራጌ ሚዲያ

17 Oct, 12:00


የጉራጌን ቱሪዝም የማነቃቃት አላማ ያለው "ጉዞ ጉራጌ 3 " በደማቅ ሁኔታ ሊካሄድ አስራ አምስት ቀናት ቀርተውታል። ይህ ጉዞ ከእስከአሁኑ በተለየ መልኩ ሙሉ ለሙሉ የክብር እንግዶችን ብቻ በመያዝ ወደ ጊቤ ፓርክና አካባቢው የሚደረግ ጉብኝት ና ካምፒንግ ነው።

አዳዲስ ነገሮች እንሞክራለን ካምፒንግ አርጎ በደን መሀል ክትፎ እንበላለን። ክትፎ ጫካ ልትገባ ነው😂 ከተፈጥሮ ሀብት አልፈንም የጉራጌ ህፃናት እየተማሩባቸው ያሉ ትምህርት ቤቶችን ና እናቶች ቀድተው የሚጠጧቸውን ወንዞች እናያለን። የጉራጌ ሁለት መልኮች 🤔

" ለዛ ቀን ያድርሰን እንጂ እንመጣለን " ካሉን መሀል ጥቂቱን ዘርዝሬላችሁ የቀሩትን ከባድ እንግዶች ደግሞ ቀጥዬ እመጣበታለሁ።

1 ሄኖክ ስዩም - የቱሪዝም ጋዜጠኛና ደራሲ

2 የሸዋ ማስረሻ - ጋዜጠኛና የሚዲያ አዋርድ አሸናፊ

3 አዳነ አረጋ - ጋዜጠኛና የሚዲያ አዋርድ አዘጋጅ

4 መሠረት በዙ - ጋዜጠኛና ዩቱዩበር

5 ሰያ ኢትዮጵያ - አስጎብኚና ጋዜጠኛ

6 Elatrik (በግሩፕ) - ቲክቶከሮች

7 በረከት ግዛቸው - ተዋናይና የጉማ አዋርድ እጩ

8 ተስፋአብ ተሾመ - ደራሲ

9 ህሊና ተክሌ - ጋዜጠኛና የሴቶች የሚታጠብ ሞዴስ አምራች

ሌሎች ታዋቂ ድምፃውያን ፣ በጎ አድራጊዎች ፣ ኢኮኖሚስቶች ናባለሀብቶች ጥሪ ቀርቦላቸዋል ። በጉዞ ደስተኛነታቸውን ገልፀው ፕሮግራማችንን እንመልከት ብለዋል ። ሲወስኑ አሳውቃችኋለሁ።

አላማችን ያስደሰታችሁ ድርጅቶች ይህን ታላቅ ጉዞ ስፖንሰር አድርጋችሁ ድርጅታችሁን አስተዋውቁ።

ጉዞው እንዲሳካ ከመቶ ብር ጀምሮ ለመደገፍ የምትፈልጉ የሀገራችን ልጆች ከታች ያለውን የጉዞ ጉራጌ አካውንት ተጠቀሙ።

ንግድ ባንክ - 1000654868097

አቤል ክፍሉ - ፂዮን አለማየሁ - ተስፋ ነዳ

Emat Gurage Media