የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ባለፉት ቅዳሜና እሁድ በአዲስ አበባና አካበቢዋ ወደ 5 አደጋዎች ደርሰው በሰውና በንብረት ላይ ጉዳታ ማድረሳቸውን አስታውቋል።
ከእነዚህ አደጋዎች መካከል በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ዋሪት አካባቢ'' የፍሊንት ስቶን ሆምስ የመኖሪያ ህንፃ ሊፍት ላይ የደረሰው አደጋ አንዱ መሆኑን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ጠዋት ላይ ሰይፉ ሾው ለመቄዶንያ ባዘጋጀው የቀጥታ ሥርጭት የገቢ ማሰባሰቢያ ላይ መረጃውን አጋርተዋል።
አደጋው የደረሰው የህንጻውን ሊፍት ተጠቅመው ከ6ተኛ ፎቅ ወደ ግራውንድ ለመውረድ ሲሞክሩ በነበሩ 14 ሰዎች ላይ እንደሆነ አስረድተዋል።
በዚህም ሊፍቱ ተበጥሶ አደጋ መድረሱን ገልጸው በዚህ አደጋ የ7 አመት ህፃን ልጅን ጨምሮ 8ቱ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ህክምና ተቋማት ለህክምና መላካቸውን አስረድተዋል።
ሊፍቱ ከሚይዘው ሰው ቁጥር በላይ ሊፍት ውስጥ ባለመግባት ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ ንጋቱ በተመሳሳይ አደጋ ከዚህ ቀደም ህይወታቸውን ያጡ ዜጎች እንዳሉም ለአብነት ጠቅሰው አስረድተዋል።
በየህንፃው የሊፍት ባለሙያ እንዲኖር በማረግ መሰል አደጋዎችን መከላከል እንደሚቻልና ኮሚሽኑም ሁሉንም ማዳረስ ባይችል የክትትል ሥራ እንደሚሰራ አስረድተዋል።
በተመሳሳይ በትላንትናው ዕለት ታዋቂው ድምጻዊ አብዱ ኪያር በተመሳሳይ አደጋ ጉዳት ደርሶበት እንደነበረና በተደረገለት ህክምናም አሁን ላይ በጥሩ ጤንነት ላይ እንደሚገኝ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።
@tikvahethmagazine