በጠላት ጥይት የቆሰለ ጓደኛው “ግደለኝ ' ጨርሰኝ…”
እያለ የሚያስቸግረው ሰው ፣ ዙሪያው በጠላት ተከቦ ማምለጫ መንገድ ያጣ ወታደር ምን ያደርጋል ?
በጠላት መድፍ እተደበደበች ከተማ ውስጥ የነበሩት
ቤተሰቦቹ በሕይወት መኖራቸውን ፡ ካሉም የደረሱበትን
የማያውቅ ሰው ምን ይሰማዋል ?
በብዙ ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ ካለው የወገን ጦር ጋር
ለመገናኘት ሳይችል ቀርቶ ፡ ውሃ ጥሙና ርሃቡ እያሰቃየው
በጠላት እየታደነ በረሃ ለበረሃ የሚንከራተት ወታደርስ ?
መጽሐፍዋ ቆራጥነትን ፡ ብልሃትን ፡ ትዕግስትን ' ጀግ
ንነትን ... በሚጠይቀው በዚህ አስቸጋሪ ስፍራ ፡ ሁኔታና
ጊዜ ውስጥ የነበሩት ገፀባህሪያት የተጫወቱትን ሚናና የደረሱበትን ግብ ታሳያለች ።
📖ጣምራ ጦር
📖ስደተኛው
📖ዕንባና ሳቅ
✍✍✍ገበየሁ አየለ