TIKVAH-ETHIOPIA @tikvahethiopia Channel on Telegram

TIKVAH-ETHIOPIA

TIKVAH-ETHIOPIA
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
1,536,931 Subscribers
59,855 Photos
1,594 Videos
Last Updated 18.03.2025 00:59

Similar Channels

🇪🇹ኢትዮ University
151,079 Subscribers
SoccerManiaET™®
12,395 Subscribers

The Role of Tikvah Ethiopia in Community Engagement and Information Exchange

Tikvah Ethiopia, known in Amharic as ቲክቫህ ኢትዮጵያ, serves as a vital platform for Ethiopian families and individuals seeking community connection and information sharing. This initiative aims to foster a sense of belonging by bringing together people from various backgrounds within Ethiopia and the diaspora. It provides a unique space for discussions, cultural exchange, and the dissemination of important news and updates that impact the Ethiopian community. Tikvah also bridges the gap between traditional communication channels and modern technology, enabling users to share messages, engage with one another, and participate in community events. As a hub of information and interaction, Tikvah Ethiopia plays a critical role in enhancing civic engagement and social connectivity among its users, while promoting various forms of cultural expression.

What is the importance of community platforms like Tikvah Ethiopia?

Community platforms such as Tikvah Ethiopia are essential in creating a space for individuals to connect and share their experiences. They foster a sense of community by allowing members to engage in conversations around mutual interests and challenges. Such platforms also serve as a repository for cultural heritage, providing a venue for sharing stories, traditions, and values that shape societal identity.

In addition to cultural exchange, these platforms can mobilize audiences for social causes, thereby raising awareness and encouraging community action. They can motivate individuals to participate in local events or initiatives, contributing to a stronger community and improved public life.

How does Tikvah Ethiopia utilize technology for communication?

Tikvah Ethiopia leverages social media to enhance communication among its members. By utilizing platforms like Facebook and Instagram, the initiative ensures that information can be distributed widely and rapidly. This facilitates immediate engagement in ongoing conversations and events, making it easier for members to stay updated.

Furthermore, the integration of various languages serves to accommodate Ethiopia's diverse population. This allows for a broader reach and engagement, ensuring that language barriers do not hinder participation and that all voices are heard.

In what ways can Tikvah Ethiopia promote cultural heritage?

Tikvah Ethiopia can promote cultural heritage by encouraging users to share their traditional practices, food, music, and art. By providing a platform for these cultural expressions, Tikvah contributes to the preservation of Ethiopian identity and promotes pride in cultural backgrounds.

Moreover, organizing cultural events or workshops through the platform enhances community engagement and allows participants to learn from one another. This kind of initiative can significantly enrich the cultural fabric of Ethiopian society, especially among younger generations who may otherwise be disconnected from their heritage.

What role does social media play in modern community building?

Social media plays a transformative role in modern community building by facilitating connections among individuals who might not otherwise meet due to geographical or social barriers. It allows for the exchange of ideas and experiences in real time, contributing to the development of virtual communities based on shared interests and values.

Additionally, social media can amplify marginalized voices, giving them a platform to express their concerns and engage in dialogue with a wider audience. This democratization of information flow is crucial in fostering inclusivity and ensuring that community narratives are diverse and representative.

How can individuals benefit from joining Tikvah Ethiopia?

Individuals can benefit from joining Tikvah Ethiopia by gaining access to a wealth of information and resources relevant to their interests and needs. The platform provides updates on community events, educational workshops, and relevant news that can enrich members' lives and foster personal growth.

Moreover, being part of a community like Tikvah Ethiopia helps individuals forge valuable connections with like-minded people, providing a support system that can be particularly beneficial for expatriates or those living in isolated environments. This social network can lead to collaborations, friendships, and networking opportunities.

TIKVAH-ETHIOPIA Telegram Channel

ቲክቫህ-ኢትዮጵያ በሚል እና በየትምክስ በሚባለው እግር እና ውስጣው ላቀማጥለን የብቻ ህዝብ ነን። ቲክቫህ-ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ስለኖርና እንባዮው ዘግናኘነት እንደሚታደግ በመሆን እናሸንፋለን። ቲክቫህ-ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ይህን ትክክለኛ መረጃን እና መልዕክቱን ስለሚሰጥ ለአዝሙድ ወይም ለተማከስን ለክፍል ቴሌግራም እንዲሁም በሌላ ስህተት ያግኙን። ለተጨባነሁት ቲክቫህ መረጋጋችንን እና ላቀማጥነትን መረጃን ለመሰረት አድርገን እናመላክምን። የሚሰሩት ለመረበን እና ያንን አገልግሎትን ከመጠበቅና ከሌላ ምስሎት ከተነሳ እናመላክም። ቲክቫህ-ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ለማንበብ በዚህ ቦታ ተከታታይ አካል መሰብሰቢያ እና መልዕክት መለዋወጫ ማንበብ እንድና ከሌላ ምስሎት መልዕክተኞችን እናከብር ቢችል፣ ዛሬ በደንብ ወኔ ምልክቱ አለ።

TIKVAH-ETHIOPIA Latest Posts

Post image

ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በዝጊቲ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ የጻድቁን ዓመታዊ ክብረ በዓል አክብረው ሲመለሱ ከደረሰው የመኪና አደጋ በሕይወት የተረፉ ምእመናንን በሶዶ ክርስቲያን አጠቃላይ ሆስፒታል ተገኝተው ጎብኝተዋል።

ብፁዕነታቸው  ለተጎዱ ወገኖች የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በሶዶ ከተማ የሚገኙ ማኅበረ ምእመናን ወምእመናት በአደጋው የተጎዱ ወገኖቻችንን እንዲጎበኙ እንዲሁም የገንዘብና የአይነት ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
#TMC

@tikvahethiopia

17 Mar, 20:04
67,113
Post image

" በእኛ ምዝገባ መሰረት የማታው በሬክተር ስኬል 5.3 ነው የተመዘገበው " - ፕ/ር አታላይ አየለ

በትላንትናው ዕለት ምሽት 3:53 ደቂቃ ላይ ጠንከር ብሎ የተሰማና በርካቶችን ያስደነገጠ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱ ይታወሳል።

እንደ የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ (USGS) መረጃ መሰረት መጋቢት 7/2017 ምሽት 3:53 የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.5 ሆኖ መመዝገቡን ባወጣው ሪፖርት ላይ ጠቅሷል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦ ፊዚክስ ህዋ ሳይንስና አስትሮኖሚ ተቋም፤ የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳይንስ መምህርና ተመራማሪ የሆኑት ፕ/ር አታላይ አየለ የማታው መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.3 የተመዘገበ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" ከምሽቱ በተጨማሪም በለሊቱ ክፍለ ጊዜም ያጋጠመውን የመሬት መንቀጥቀጥ በምን ያህል ሬክተር ስኬል እንደተለካ ለማወቅ እየሰራንበት ነው ማንዋል ስለሆነ የምንሰራው ይዘገያል " ብለዋል።

ፕ/ር አታላይ፤  " መንቀጥቀጡ በሬክተር ስኬል አነስ አነስ አለ እንጂ ያቋረጠበት ጊዜ የለም እኛም እየመዘገብን ነው ድግግሞሹ ቀንሷል አልፎ አልፎ ግን ከፍ ያለ ይፈጠራል ተከታዮቹም እንደ ድሮ የበዛ አይደለም መጠኑ ዝቅ ያለ ሆኖ ብዙ ኪሎ ሜትር የሚሰማበት ጊዜ አለ መጠኑ ከፍ ያለ ሆኖ ብዙ የማይሰማበት ጊዜ አለ " ብለዋል።

ይህ አይነት ንዝረት መቼ ይቆማል ? ስንል ላነሳንላቸው ጥያቄም " እንዲህ እንዲህ እያለ ያቆማል በዚሁ አይቀጥልም በዚህ ጊዜ ያቆማል ብሎ ማስቀመጥ ግን ከመላምት በዘለለ በእርግጠኝነት ማስቀመጥ አይቻልም ዛሬ ጨመረ ቀነሰ ብለን በስጋት የምንኖርበት አይደለም የከፋም ሊሆን ስለሚችል " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

አክለውም " ከእኛ የሚጠበቅብንን አድርገናል ከስር ከስር እየመዘገብን እያሳወቅን ነው ስራው ማንዋል ነው ምርምርም ይፈልጋል ባለው ሃብት እየታገልን ነው " ብለዋል።

" ብዙ ጊዜ በሌላው ዓለም እንደዚህ አይነት ነገር ሲፈጠር እንደመልካም አጋጣሚ የሚጠቀሙበት ነው ብዙ ፈንድ ይመጣል አቅም ይገነቡበታል የምርምር ተቋማታቸውን የሚያጠናክሩበት ነው እኛ ጋር ግን እስካሁን ምንም ጠብ ያለ ነገር የለም " ሲሉ ጉዳዩ ስለተሰጠው የትኩረት ማነስ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

" መስክ ወጥተን የመረጃ መሰብሰቢያ ጣቢያዎቻችንን ሰርቪስ አድርገን ተመልሰናል ግን አቅም ይገነባል ብለን በምናስብበት ሰዓት ጭራሽ አቅም በሚያዳክም መልኩ የመስክ መኪኖቻችን በዩኒቨርስቲ ማኔጅመንት እንዲቀሙ ተደርጓል " ነው ያሉት።

በተጨማሪም " ተፈጥሮ ሁል ጊዜ አማክሮ አይመጣም የተፈጥሮ ክስተት በራሱ መንገድ በራሱ ጊዜ የሚመጣ ነው የከፋ ክስተት እና አደጋ ሊከሰት ይችላል የከፋው ቢመጣ ምን ያህል ተዘጋጅተናል የሚለውን ግንዛቤ ውስጥ መክተት ያስፈልጋል " ብለዋል።

" ሊከሰት ቢችል ምን ምን አይነት እርምጃዎችን ለመውሰድ ተዘጋጅተናል ? የዓለም ተሞክሮስ ምን ይመስላል ? የሚለውን በመመልከት አቅም መገንባት መሳሪያዎችን ማዘጋጀት ባለሞያዎችን መደገፍ መደረግ ያለባቸው ነገሮች መደረግ አለባቸው " ሲሉም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

17 Mar, 19:58
67,597
Post image

#አፋር 🕊 #ሶማሌ

" እኛ እና ሶማሌዎች ከሚያለያዩን ነገሮች ይልቅ አንድ የሚያደርጉን ነገሮች በትልቁ ይበዛሉ " - ሀጂ አወል አርባ

ዛሬ በአፋር ክልል መዲና ሠመራ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ሕዝቦች የኢፍጧር ስነስርዓት ተካሂዷል።

በስነ ስርዓቱ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች፣ የሰላም ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ  ፣ የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት ሙስጠፋ ሙሁመድ እና ሌሎች የክልሉ ባለስልጣናት ተገኝተው ነበር።

የአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ሀጂ አወል አርባ " እኛና ሶማሌዎች ከሚያለያዩን ነገሮች ይልቅ አንድ  የሚያደርጉን ነገሮች በትልቁ ይበዛሉ " ሲሉ ገልፀዋል።

ስነ ስርዓቱ የሁለቱን ክልል ወንድማማቾች የመተሳሰብ ፣ የአብሮነት እና የፍቅር ተምሳሌት ለማድረግ መካሄዱን ጠቁመዋል።

" ትላንት በሠው ሠራሽ ችግሮች የተፈጠሩትን ግጭቶችን ዛሬ የማስቆም ታሪካዊ ሀላፊነት የኛ ነው " ያሉ ሲሆን "  በኛ ትውልድ ከዚህ ቀደም ያለውን ጥላቻና መራራቅን የምንቀይርበትና የምናሻሽልበት ዘመን ነው " ብለዋል።

" ክፋትን ወደ ፍቅር እንቀይራለን ለዚህ ማሳያው ደግሞ የጅጅጋው እና የዛሬው የኢፍጣር ፕሮግራም ማሳያ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ፤ " ሁለታችንም ክልሎች በቀድሞው ስርዓት የተገፋን እና ከልማት የተገለልን ነበርን " ሲሉ ተደምጠዋል።

" በለውጡ ዘመን ያገኘነውን መሻሻል ተጠቅመን ከግጭት እና ከጥላቻ ወጥተን በአብሮነት ወደ ልማት እና ወደ ብልፅግና ተያይዘን እና ተደጋግፈን ያለንን የሠው ሀይል በጋራ በማድረግ ክልላችንን ማልማት አለብን " ሲሉ መግለጻቸውን የአፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል።

#AfarMassMediaAgency

@tikvahethiopia

17 Mar, 19:55
63,059
Post image

የክላርኔቱ ንጉስ መርዓዊ ስጦት !

እጅግ በጣም አድማጭን በሚመስጡና በአድማጭ በሚወደዱ የክላርኔት ጨዋታቸው የሚታወቁት ሙዚቀኛ መርዓዊ ስጦት በህመም ምክንያት ከዚህ ዓለም በ90 ዓመታቸው በሞት ተለይተዋል።

በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴአትር ከ60 ዓመታት በላይ በተለይ በክላርኔት ጨዋታ ይታወቁ ነበር።

ከክላርኔት መጫወት ባለፈ የግጥምና ዜማ ደራሲነት እና አቀናባሪነት ይታወቃሉ።

ሙዚቀኛ መራዊ 1928 ዓ.ም በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን በአምባሰል ወረዳ ነው የተወለዱት።

ሙዚቀኛ መርዓዊ ስጦት በሞያቸው በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ የተለያዩ ሽልማቶች አግኝተዋል፡፡

@tikvahethiopia

17 Mar, 19:55
60,164