ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት @frehaymanotss Channel on Telegram

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

@frehaymanotss


በብ/ዓ/ቅ/ጴጥሮስ ወጳውሎስ እና ቅ/ገብርኤል ቤ/ክ የፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ገጽ ነው

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት (Amharic)

ምንድን ነው ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት? ስለዚህ በግንባር እና ቅኔህላችን እባላለሁ። ይህ ስልኩን ትምህርት ምስክርነት መረጃ ማለት ያለው እንደሆነ የትምህርት አስተዳደር ስለነበር ከግንባታችን ይጠቀሙ። ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት ገጽ በበጎ ስልክ ላይ ያግኙ። ተጨማሪ የትምህርት ዕቅድ መረጃዎችን ይከናወን። ስለተጨማሪነት ለመግባት የምንጠቅሱበት ሰው የሚፈልግ ማንኛውም መረጃ እንደሆነ የትምህርት ሙሉ መማር እንዲረጋግ ይረዳናል።

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

10 Feb, 06:54


#ኑ_አብረን_እንቅረብ

🍀 ሰላም ለእናንተ ይሁን 🍀

በፍ/ሃ/ሰ/ት/ቤት የጸሎት ፣ምክር እና ንስሐ ክፍል አዘጋጅነት የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ እና ክቡር ደም በጋራ እንቀበል የዘላለም ህይወትን እናገኝ ዘንድ #ኑ_አብረን_እንቅረብ በማለት መንፈሳዊ ግብዣን ይጋብዛችኋል።

የጸሎት እና የትምህርት ቀናት :-

⌛️ከ የካቲት 3 - 5 /2017 ዓ.ም

#ኑ_አብረን_እንቅረብ የሚከናወንበት ቀን

🗓 የካቲት 23/2017 ዓ.ም



ለበለጠ መረጃ እና ጥያቄ
📲 0922158954

📲 0964140684
📞ይደውሉ



"  እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን አሁን ነው።"
(፪ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች ፮÷፪)

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Feb, 23:25


ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
ተናፋቂው ጉባኤያችን ከሁለት ወር ቆይታ በኋላ በልዩ ሁኔታ ተዘጋጅቷል።
በዕለተ እሑድ የካቲት 9
ከ11:00-1:00
በመ/ር ብሩክ ተክሉ
ነገረ ቤተ ክርስቲያን በሚል ርዕስ ሰፊ ዳሰሳ የምናደርግ ይሆናል።
ከወዲሁ ቀጠሮዎን ያስተካክሉ

የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን።

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

08 Feb, 07:25


ሰላም እንደምን ቆያችሁ ውድ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ ሚዲያ ቤተሰቦች። ሚዲያችን ላለፉት ሰባት ቀናት ያህል የጥምቀት በዓልን አስመልክቶ ሲያወዳድር የነበረውን የፎቶ ግራፍ ውድድር የምርጫ ጊዜ የተጠናቀቀ መሆኑን እያሳወቅን አሸናፊዎችን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል። በፎቶ ግራፍ ውድድሩ ላይ ለተሳተፋችሁ እንዲሁም በመምረጥ ድምጻችሁን ለሰጣችሁ ሁሉ በልዑል እግዚአብሔር ስም ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። መልካም ዕለተ ሰንበት ይሁንልን።

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

👉 Youtube

👉 Facebook

👉 Telegram

👉 Tiktok

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

06 Feb, 19:08


በደብራችን በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ወ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት በነበረን የጥምቀት በዓል አገልግሎት የሰንበት ትምህርት ቤታችን የጀርባ አጥንት የሆነው ሚዲያ ክፍላችን በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU ለይ ለውድድር ካቀረብናቸው 5 ፎቶዎች መካከል ይህ ፎቶ ስለተመረጠ የናንተ ድምጽ እጅግ እጅግ አስፈላጊ ነው ስለሆነም በተዘጋጀልን የመወዳደርያ ኮድ 005  በመምረጥ ሰንበት ትምህርት ቤታችንን እንደግፍ ። አንድ ድምጽ ዋጋ አላት

ፍሬ ሃይማኖት ሚዲያ ክፍል

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

09 Jan, 11:45


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ለሰንበት ት/ቤቱ አባላት በሙሉ
የፊታችን አርብ ቅዳሜና እሁድ(ጥር 2, 3 እና 4) ልብሰ ሰብሐት ስለምናጥብ የምትችሉ አባላት መጥታችሁ በማጠብ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ በሐዋርያቱ ስም ጥሪ እያስተላለፍን በአጠባው መሳተፍ የማትችሉ አባላት በቁሳቁስ መደገፍ (ሳሙና, ኦሞ, ላርጎ) የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ሒሳብና ንብረት ክፍል

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

08 Jan, 16:31


ዲያቆን ኢዮብ ፈይሳ

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

08 Jan, 16:10


የሐዘን መግለጫ

ሕያው ሆኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ማን ነው ። መዝ 89፥48

የሰ/ት/ቤታችን አባል የሆነው ዲያቆን ኢዮብ ፈይሳ በድንገት ስላረፈ ነገ ሐሙስ በ01/05/2017 ዓ.ም በሱሉልታ ወሰርቢ ሪል ስቴት አካባቢ በሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 06:00 ሰዓት የቀብር ሥርዓቱ ይፈጸማል ።
ቅዳሜ ከቀኑ በ09:00 በሱሉልታ አትሌቶች መንደር በመኖርያ ቤታቸው በመገኘት ሐዘንተኞችን ስለምናጽናና የሰ/ት/ቤቱ አባላት በሙሉ እንድትገኙ ።
ለቤተሰቦቹ እግዚአብሔር አምላክ መጽናናትን ይስጥልን ።
" ኢየሱስም ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል ። " ዮሐ 11፥25

ለበለጠ መረጃ ፦ 09-13-75-55-83 ዲና
09-00-66-41-96 ዮናስ

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

04 Jan, 09:39


እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን
👉እንደተለመደው በታኅሣሥ 29 ወደ ሸገር ማረሚያ ቤት ሄደን በዓልን ከታራሚዎች ጋር ስለምናሳልፍ አብራችሁን መሄድ የምትፈልጉ ከሥር በተቀመጠው ስልክ ደውላችሁ ተመዝገቡ።
👉የትራንስፖርት ዋጋ 200ብር (መሄጃ እና መመለሻ)
👉መምጣት የማትችሉ ነገር ግን ታራሚዎችን በተለያየ ቁሳቁስ ማገዝ ወይንም በኛ በኩል መላክ የምትፈልጉ ደውሉልን

☎️ +251904202380
☎️ +251912455595

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

30 Dec, 11:22


ሠላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
በሰ/ት/ቤታችን ለአጭር ጊዜ የሚቆይ የምልክት ቋንቋ ትምህርት ተዘጋጅቷል።
እርሶም በዚህ እድል ተጠቃሚ ሆነው ይጠቀሙ ዘንድ አስቀድመው ይመዝገቡ።

ከስር በተቀመጠው ሊንክ እና በመደበኛ መርሐግብር ክፍል ይመዝገቡ።
@ethnati

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

30 Dec, 07:26


በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

ለሰ/ት/ቤታችን አባላት በሙሉ

በሰ/ት/ቤቱ ውስጥ ለአገልግሎት የምትጠቀሙበት ሎከር ያላችሁ ክፍላት ወይም አባላቶቻችን የሎከራችሁን አንድ ቁልፍ ለንብረትና ሒሳብ ክፍል ከዛሬ ታህሳስ 21 እስከ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንድታስረክቡ እየጠየቅን ይህ ባይሆን ግን ሒሳብና ንብረት ክፍሉ የሎከሮቹን ቁልፎች በራሱ በመተካት ሎከር እየጠየቁ ላሉ ክፍሎች እንደሚሰጥ እንገልፃለን፡፡
ሒሳብና ንብረት ክፍል

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

18 Nov, 10:59


ሰላም ለእናንተ ይሁን
ዛሬ በኅዳር 8/2017 ዓ.ም በነበረን የቅዱስ ገብርኤል የጥምቀት የቃና ዘገሊላ እንዲሁም የቅዱስ ጊዮርጊስ የመዝሙር ጥናት የመክፈቻ መርሐግብር ከ110 በላይ ነባር እና አዳዲስ አባላት በተገኙበት ተከናውኗል የሰ/ት/ቤቱን ጥሪ ሰምታችሁ ለተገኛችሁ ሁሉ አምላከ ቅዱሳን ያክብርልኝ
በመርሐግብሩም
👉መምህር ኢዮብ ዘገነተ ጽጌ ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
👉የመዝሙር መምህራን ዝማሬ እንዲሁም በበገና ክፍል ዝማሬ በበገና የቀረበ ሲሆን 
👉ቀሲስ ያሬድ መለሰ በመርሐግብሩ ተገኝተው ቡራኬ በመስጠት  የመዝጊያውን ጸሎት አከናውነውልና።
በዕለቱ በተለያየ ምክንያት ያልተገኛችሁ አባላት ከነገ ጀምሮ የጥናት መርሐግብሩ የሚቀጥል መሆኑን ለማስታወስ እንወዳለን።

👉ለነባር አባላት ከዓርብ ውጪ ከ12:00--1:30
👉ለአዳዲስ አባላት ከ11:00 ጀምሮ

👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/mezmur_fere
👆👆👆👆👆👆👆
ጆይን በማድረግ አዲሱን የመዝሙር ክፍል ቻናል ይቀላቀሉ።

መዝሙር ክፍል
08/03/2017 ዓ.ም

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

15 Nov, 11:12


https://forms.gle/kuA9HpzLBtTGJMcW7

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

14 Nov, 09:50


ማስተካከያ
በአባላችን ህልፈት ምክንያት ሀዘንተኞችን ለማጽናናት ከ6/03/2017 ምሽት ጀምሮ ተብሎ የተለጠፈው ማስታወቂያ ማስተካከያ ተደርጎበት ከዛሬ ምሽት ማለትም ከ05/03/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀን ተብሎ ይስተካከል፡፡

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

13 Nov, 15:30


የሐዘን መግለጫ
ሕያወ ሆኖ  የሚኖር ሞትንሰ  የማያይ ማን ነው
(መዝሙረ ደዊት  89/48 )

የሰ/ት/ቤታችን አባል የሆነችወ  እህታችን  ዮዲት   ደጀኔ ሰላርፉ  ነገ ሃሙስ  በብርሃናት  ዓለም ቅዱሰ ጴጥሮሰ ወጳወሎሰ  ወቅዱሰ  ገብርኤል  ቤ/ከ   ከቀኑ  በ6:00 ሰዓት ላይ  የቀብር ስነ ስርዓት  ስለሚከናወን  የሰንበት  ትምህርት  ቤቱ  አባላት  በመኖሪያ ቤታቸው 5:00 ሰዓት ላይ እንድትገኙ !!!
ከአርብ ጀምሮ እስከ እሁድ ለተከታታይ ለሦስት ቀናት ከምሸቱ  11:00  ሰዓት   በመኖሪያ  ቤታችው  በመገኘት    ሐዘንተኞችን  ሰለምናጽናና የሰንበት ትምርት ቤቱ  አባላት   እንደትገኙ ስንል  ለቤተሰቦቿ  እግዚአብሔር  መፅናናትን  ይሰጥልን
“ኢየሱስም  ትንሣኤና  ሕይወት  አኔ  ነኝ   የሚያምንብኝ  ቢሞት  እንኳን ሕያው  ይሆናል” 
      “የ ዮሐንሰ  ወንጌል   11 :25”

      አድራሻ  ከኪዳነ ምሕረት ጠበል ቦታ ባለው ቅያስ ማሩታ ሆቴል አጠገብ

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Nov, 07:19


ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወቅዱስ ጳውሎስ ወገነተ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት
የአካባቢ ወጣቶች ጉባኤ ተጀመረ
በዕለተ እሑድ 08/03/2017
በ5:00 በሰ/ት/ቤቱ አዳራሽ በልዩ የመክፈቻ መርሐ ግብር ይጀምራል በእለቱ ወዳጆትን ጠርተው በጉባኤው ይገኙ።

የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን።

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

12 Nov, 07:17


በ8ኛ ዙር እንገናኝ
ጉባኤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 7ኛ ዙር መርሐ ግብር " ነገረ ቅዱሳን በነገረ ድኅነት " በሚል ርዕስ በርካታ ሰዎች በተገኙበት ተከናውኗል።

አምላክ ቢፈቅድ እና ቢወድ በቀጣይ ወር ይቀጥላል።

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

11 Nov, 10:28


ሰላም ለእናንተ ውድ የፍሬ ሃይማኖት ሰ/ት/ቤት አባላት
ኑ በዝማሬያችን /በምስጋናችን/የኢያሪኮን ቅጥር እናፍርስ
ኑ አብረን በፍቅር አገልግለን ከፍቅር አምላክ በረከት እናግኝ።

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Nov, 16:05


የሐዘን መግለጫ
ሕያወ ሆኖ የሚኖር ሞትንሰ የማያይ ማን ነው
(መዝሙረ ደዊት 89/48 )

የሰ/ት/ቤታችን አባል የሆነችው የእህታችን ቅድስት ገላዬ ባለቤቷ ሰላርፈ ነገ ረቡዕ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ
በመኖሪያ ቤታችው በመገኘት ሐዘንተኞችን ሰለምናጽናና የሰንበት ትምርት ቤቱ አባላት እንደትገኙ ስንል ለእህታችን እንዲሁም ለቤተሰቦቻቸው እግዚአብሔር መፅናናትን ይሰጥልን!
“ኢየሱስም ትንሣኤና ሕይወት አኔ ነኝ፤ የሚያምንብኝ ቢሞት እንኳን ሕያው ይሆናል”
“የ ዮሐንሰ ወንጌል 11 :25”

አደራሻ፡- ቅዱስ ፊሊጶስ ቤ/ክ ወረድ ብሎ ሾላው ምንጭ አጠገብ ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡-0913982026

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

05 Nov, 14:48


ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች
ጉባኤ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 
ሕዳር 1 "ነገረ ቅዱሳን በነገረ ድኅነት" በተሰኘ ርዕስ ከእናንተ ጋር ልትወያይ ዝግጅቷን ጨርሳለች።

እርሶ በዕለቱ ወዳጆትን ጋብዘው በሰዓቱ ይገኙ
ጉባኤው ስለ ነገረ ቅዱሳን
ቅዱሳን በድኅነታችን ያላቸው ሱታፌ እነዚህን እና ሌሎች ሰፊ ጉዳዮችን ይዳስሳል እንዳይቀሩ።

ቀን ኅዳር 1
ሰዓት 11:00-1:000
የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

01 Nov, 06:41


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱአምላክ አሜን!
ማስታወቂያ
በሰንበት ት/ቤታችን ከሚገኙ ክፍላት መካከል አንዱየሆነው ሚዲያ ክፍል የፎቶ እና የቪዲዮ ቀረጻአገልግሎቶች እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ከ 2016 ዓ.ም የጥምቀት በዓል ጀምሮ በደብራችን በተለያዩጊዜያቶች የተከበሩ ክብረ በዓላት ላይ የተነሱትን የተለያዩፎቶዎች በሶፍት ኮፒ መውሰድ የምትችሉ መሆኑንእያሳወቅን አገልግሎቶቹን ለማግኘት ከዚህ በታችበተገለጸው የቴሌግራም አድራሻ በመግባት ሙሉስማችሁን እየጻፋችሁ ስትልኩልን ፎቶዎችን መርጠንየምንልካልችሁ መሆኑን በማክበር እናሳውቃለን፡፡
አድራሻው፡- @freh2017
ሚዲያ ክፍል

ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት

19 Oct, 17:45


https://youtu.be/hwZcZyGtQak

2,797

subscribers

2,746

photos

24

videos