ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons @ethioicons Channel on Telegram

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

@ethioicons


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ ስለታሪካቸው፣ ሃይማኖታዊ ትርጉማቸው፣
አሣሣል መረጃ የሚያገኙበት ቦታ፡፡ A channel that discusses about icons of ethiopian orthodox tewahido church. Contact for questions @shihaile or [email protected] or www.ethioicons.wordpress.com

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons (Amharic)

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons ብሎ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ ስለታሪካቸው እና ሃይማኖታዊ ትርጉማቸው ለማንኛውም ጥያቄ ወይም ማቅረብ የጀመረው ቦታ፡፡ ይህ ፋሲል በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሥዕላት እንደመለየ የተሟሉ አካባሚዎችን ይስማማ ይከታተሉ እና በመንገድ ላይ ረጅማን ያልተገኙ ገጽታዎችን እና ተመልከቱ ሰጥተዋል። መረጃ ለጥናት @shihaile ወይም [email protected] ወይም www.ethioicons.wordpress.com ላይ ይደውሉ።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

04 Feb, 10:18


ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons pinned «»

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

01 Feb, 08:58


ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons pinned «»

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

29 Jan, 05:03


+++ሥዕለ እረፍታ ለማርያም+++

በሠዓሊ ኃይለ ማርያም ሽመልስ (በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ አማካሪ፣ ጥናትና ሒስ አድራጊ) 0913 05 2824

++++++++++===+++++++++++
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእረፍት በዓል አደረሳችሁ። ከሥር የእመቤታችን የእረፍትና የግንዘት ታሪክን መሠረት በማድረግ ትውፊቱን ጠብቀው የተሣሉ ጥንታዊያን የብራና፣ የእንጨት ገበታ (ኢቆና)፣ እና የግድግዳ ቤተ መቅደስ ሥዕሎች ቀርበዋል።

የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል እንደተሣለበት መደብ እና ያለው የቦታ ስፋት የሚጨመሩ ወይም የሚቀነሱ አካላት አሉበት።

በአጠቃላይ ሲሣል የእመቤታችን ቅዱስ ሥጋ በክብር አልጋ ላይ ሆና (ተቀምጣ / ጋደም እንዳለች)፤
ቅዱስ ነፍሷን ጌታችን በእልፍ አእላፍ መላእክት ተከቦ ሲቀበላት፤
ቅዱሳን ሐዋርያት እያዘኑ ከበዋት መብራት አብርተው፣ መጽሐፍ እያነበቡ እና እያጠኑ፣ ቅዱስ ጷጥሮስ በግርጌ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራስጌ ሆነው፣
ቅዱሳን መላእክት እያጠኑ፣
ቅዱሳን ደናግል አዝነው፣
ቅዱስ ዳዊት በገና እየደረደረ፣ ቅዱስ እዝራ በመሰንቆ እያመሰገነ በአጠቃላይ በአስደናቂ መንፈሳዊ ደስታ ይሣላል።

ማስታወሻ፥ የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል ላይ ታውፋንያን አስገብቶ መሣል ጸያፍና ተገቢ ያልሆነ ነው። ምክንያቱም ስንክሳር፣ ተአምረ ማርያም ሆነ ሌሎች አዋልድ መጻሕፍት እንደሚነግሩን ታውፋንያ በዚህ በተቀደሰ መንፈሳዊ ስፍራ አስቀድሞ አልነበረም።

የቤተ ክርስቲያን የሆኑት ቅዱሳት ሥዕላት እንወቅ፣ እንመልከት እና እንጸልባቸው። በስጦታ ይሁን  ወይም በስእለት ለቤተ ክርስቲያንም እንስጥ።


ጥንታዊ ቅዱሳት ሥዕላት ለማየት ለማውረድ፣ ለሌሎች ለማጋራት ከፈለጉ @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

09 Jan, 07:13


በጣም ድንቅ አኒሜሽን ስለ ቅዱሳት ሥዕላት ክብር የተዘጋጀ በኢትዮጵያ ጃንደረባ። በውስጡ የተላለፈው መልእክት የታሪክ ፍሰት እና ዝግጅት (Art direction) በጣም ግሩም ነው ገብታችሁ ተመለከቱት ብዙ ታተርፋላችሁ። በውስጡ ስለሚገኝ ለማሳያ የቀረቡት ሥዕሎች ላይ ደግሞ በሞያዊ ሒስ በቪድዮ እና ጽሑፍ እመለሳለሁ እስከ ዚያ ታጋበዙልኝ። ለቤተ ክርስቲያን ጥበብ ዘመኑን ዋጅቶ ማስተዋወቅ እንደዚህ ይገባል። https://youtu.be/Wj7kJJhrd4s?si=0LxwWmN--LNKqbPG

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

09 Jan, 00:52


Channel photo updated

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

07 Jan, 13:59


እንኳን ለብርሃነ ልደቱ ሁላችንንም አደረሰን። በዓሉ የደስታ እና የሰላም ከኃጢአት በንስሐ የምንመለስበት ያድርግልን። እግረ መንገዱም የጾም ወራት ቢያልቁም ከክፋት መጾም ሳንረሳ በዓሉን እንድናከብር እግዚአብሔር ይርዳን። 

በሀገራችንም በተለያዩ ስፍራዎች በረሀብና ችግር ያሉትንም በማሰብ የልደት ወቅትን እንድናከብር ፈቃዱ ይሁን።

መልካም ገና ይሁንልን ለሁላችን።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

07 Jan, 06:55


የቅዳሴን ጥልቅ ትርጉም እንድንረዳ ይህንን ድንቅ ተከታታይ ባለ ሰባት ክፍል ቪድዮ ተመልከቱት። ብዙ ታተርፉበታላችሁ። በእውኑ በጻፍኩት ሀሳብ ያሳዘንኳችሁ በጌታችን ፍቅር ይቅርታ እጠይቃለሁ። ግን ቤተ ክርስቲያንን እንወቃት እንቅመሳት ያኔ ከቅዳሴ መለየትን እንደሞት እንቆጥረዋለን።

ከላይ የተጻፈው ሀሳቤ ግልጽ ካለሆነ በጽሑፍ በድምጽ ምላሽ ሳላቀረብኩ ኮሜንት ላይ ገብታችሁ ሀሳቤን የበለጠ ትረዱታላችሁ።

ቪዲዮቹን ለመመልከት እና ተጨማሪ ተከታታይ የሌሎች መምህራንን ለመልቀቅ እንዲመች ቻናል ስለከፈትኩ እዚያ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ። https://t.me/kidase27

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

01 Jan, 14:37


በቅርቡ ከኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት «@ethioicons» ገጽ ይጠብቁን።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

01 Jan, 05:24


ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons pinned «በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። ወድ የቤተ ክርስቲያን ልጅ ባለፉት የተወሰኑ ወራት ውስጥ ትንሽ ከበድ ያለ ሕመም ገጥሞኝ ስታከም ነበር። በዚህም አንዳንድ ሥራዎች ላይ መደራረብ ፈጥሮብኝ እንደማስበው ትምህርቶች በሥዕላት ዙርያ መልቀቅ አልቻልኩም። እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በቀጣይ ከተለያዩ ወንድምና እህቶች በቪድዮም ትምህርት ይሁን አስተያየቶች ስለቀረቡልኝ ከጽሑፍ በተጨማሪ በቪድዮ…»

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

01 Jan, 05:23


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

ወድ የቤተ ክርስቲያን ልጅ ባለፉት የተወሰኑ ወራት ውስጥ ትንሽ ከበድ ያለ ሕመም ገጥሞኝ ስታከም ነበር። በዚህም አንዳንድ ሥራዎች ላይ መደራረብ ፈጥሮብኝ እንደማስበው ትምህርቶች በሥዕላት ዙርያ መልቀቅ አልቻልኩም።

እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ በቀጣይ ከተለያዩ ወንድምና እህቶች በቪድዮም ትምህርት ይሁን አስተያየቶች ስለቀረቡልኝ ከጽሑፍ በተጨማሪ በቪድዮ በቲክቶክ እና ዩቲዩብ ላይ እመጣለሁ።

ከዚህ በፊት በነበረው መጠይቅ ላይም በስልክ እና በሜሴጅ እንደመረጣችሁት እነዚያን ርእሶች ይዤ የምመጣ ይሆናል።

ከወዲሁ ላሳውቅ የምፈልገው በቀጣይ የሚቀርቡ ትምህርቶች ላይ በመረጃ ላይ ብቻ ትኩረት ያደረገ እንጂ ግለሰብ ወይም ተቋም ላይ ያለነጣጠረ መሆኑ ነው።

ይሁን እንጂ ሰው እንዳይከፋው እያልኩኝ ላለፉት 10 ዓመታት ጀምሮ ዝም ያለኩትና ሳዝንባቸው የነበሩ ጉዳዮችን በይፋ የሚወጡ ይሆናል። ለቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ቀኖና ብናደላ ይገባናል

ስለዚህ ወገባችን ታጥቀን ለመማርና ለውጥ ለማምጣት እንዘጋጅ። አስተያየትም በጨዋነት የምንለዋወጥ ይሆናል።

መልካም የሠሩ ይመሰገናሉ የሚያበላሹ እንዲያስተካከሉ በመረጃ ተደግፈን እናግዛለን።

እምቢ ብለው ግን በማናለብኝነት የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ለሚንዱ ግን በመረጃ የሳሉት ሥዕል ስህተትነት ምእመናን እንዲያውቁና እንዳይጠቀሙ እናስተምራለን።

ተሐድሶን የምንከላከለው በመሞዳሞድ ሳይሆን ፊት ለፊት ተጋፍጦ ለቤተ ክርስቲያን ትውፊት በመቆም ነው።

የቅዱስ ዮሐንስ፣ የቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊና የአቡነ መብዓ ጽዮን በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

15 Dec, 08:34


የሰማዕቷን ቅድስት አርሴማ ሥዕል በሠዓሊ ኃይለማርያም ሽመልስ (@ethioicons @shihaile) ተስሏል። 

የተሣለው ለደብረ ወርቅ ዋዱ ቅድስት ቁስቋም ቤተ ክርስቲያን በ2017ዓ.ም. ነው። የሥዕሉ ምስጢር ከስር ቀርቧል።

1. መልአኩ ከላይ መሆኑ ከፍ ያለና ሰማያዊ የሰማዕትነት አክሊልን እንደተቀበለች ለማመልከት ነው። ይህ ደግሞ በጣና ገዳማት መልአኩ ባለበት ስፍራ አክሊል ሲወርድላት ከተሳለው ሥዕል መነሻ በማድረግ የተሣለ ነው።

2. በስተግራ እመ ምኔት ቅድስት አጋታ ክብሯን እንድትጠብቅ ስትነግራት ይታያል። በስንክሳር ላይም የተመዘገበውን ምክሯን በመልእክት መልኩ ይዛ ትታያለች።

3. ከቅድስት አጋታ አጠገብ የእጅ ስራ አብራ የነበረች ደንግል ተስላለች። ይህንን የእጅ ስራ እየሸጡ ለእለት ምግብ ይውሉ እንደነበር ስንክሳሩ እንደሚገልጸው። ይህንንም ለመጠቆም በእጇ ብልቃጥ ይዛ ትታያለች።
በተጨማሪ ሌሎች ደናግል ሰማዕታት አብረው ይታያሉ።

4. በስተቀኝ በኩል ደግሞ ቅዱስ ጎርገርዮስ የፓትርያርክ ቆብ አድርጎና ልብሰ ተክህኖ ለብሶ እና ወንጌልን ይዞ ይታያል። ይህም ወንጌል በሀገረ አርማንያ ያዳረሰ መሆኑን ያጠይቃል።

5. ቅዱስ ድርጣድስ ደግሞ ዘውድ አድርጎ በእጁ ዓለምን ይዞ ይታያል። ይህም ንግሥናውን እና በግዛቱ ወንጌል እንዲስፋፋ ማድረጉን ያመለክታል።
ከእርሱ አጠገብ ያሉት ደግሞ ከአርሴማ ጋር አብረው የነበሩ ወንድ ሰማዕታት ይወክላሉ።

6. ከጀርባ ደግሞ የምንመለከተው ቤተ ክርስቲያን በንጉሥ ድርጣድስ ፈቃድና በቅዱስ ጎርጎርዮስ አማካኝነት የታነጸው ሕንጻን ይወክላል። ይህች ቤተክርስቲያን ደግሞ የቅድስት አርሴማ፣ ቅድስት አጋታና የደናግል ሰማዕታት ቅዱስ አጽም ማረፊያን ትወክላለች።

በአጠቃላይ በስተግራ ሰማዕትነቷን በስተቀኝ ደግሞ ቅዳሴ ቤቷን በማሰብ ተሥሏል።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

15 Dec, 08:33


በሠዓሊ ኃይለማርያም ሽመልስ (@ethioicons @shihaile)

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን፡፡

እንኳን ለቅድስት አርሴማና ለተከታዮቿ ሰማዕታት የፍልሰትና የቅዳሴ ቤት መታሰቢያ  በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የቅድስት አርሴማ ገድልና ታሪኳን ጠብቆ ጥንታዊ የተሳሉ ሥዕሎችን መሠረት በማድረግ የተሣለ ሥዕል ትርጉም ከአጭር የሰማዕቷ ተጋድሎ ጋር ከስር ቀርቧል።

*ቅድስት አርሴማ እንደ ልጅ ወላጆቿን በመታዘዝ ደስ ያሰኘች ቡርክት ናት::
*ቅድስት አርሴማ ይሕ ቀረሽ የማይሏት ውብ ናት::
*ቅድስት አርሴማ ድንግል ናት::
*ቅድስት አርሴማ ባሕታዊት ጻድቅ ናት::
*ቅድስት አርሴማ ኃያል ሰማዕት ናት::

ዲዮቅልጢያኖስ በመልኳ ተማርኮ ቅድስት አርሴማን ካላገባሁ በማለቱ  ድንግሏን አርሴማን ጨምሮ ክርስቲያኖችን ወደ አርማንያ ተሰደዱ። በአርማንያም በአንድ ገዳም ውስጥ ተደብቀው በጾምና በጸሎት ለጥቂት ጊዜ ቆዩ።

ዲዮቅልጢያኖስ ቅዱሳኑ ወደ አርማንያ መሔዳቸውን ስለ ሰማ ይዞ እንዲልክለት ድርጣድስን ላከው። ድርጣድስ ግን ቅድስት አርሴማን ባያት ጊዜ ከውበቷ የተነሳ መታገስ ባለመቻሉ "ካላገባሁሽ" አላት።

ድንግሊቱ ግን "እኔ የክርስቶስ ሙሽራ ነኝ: አይሆንም" አለችው:: ሊያስፈራራት ሞከረ:: ዐይኗ እያየ ደናግሉን ጨፈጨፋቸው::

አልሳካልህ ቢለው በአደባባይ በግድ ሊያገባት ቢሞክር እጁን ጠምዝዛ በሰው ሁሉ ፊት መሬት ላይ ጣለችው:: እጅግ ስላፈረ አስገረፋት: አሰቃያት: ዐይኗንም አወጣ:: በመጨረሻም አንገቷን አስቆርጦ ከሰማዕታቱ ጋር ተራራ ላይ ጣላት::

+ከነገር ሁሉ በኋላ ድርጣድስና ባለሟሎቹ ለአደን በሔዱበት ርኩስ መንፈስ ወደ አውሬነት (እሪያነት) ቀየራቸው። የንጉሡ እንስሳ (አውሬ) መሆን በአርማንያ ታላቅ ድንጋጤን ፈጠረ።

የንጉሡ እህት ስታለቅስ በራዕይ "ለእመ ኢያዕረግምዎ ለጐርጐርዮስ አልብክሙ ድኂን-ጐርጐርዮስን ከተቀበረበት ካላወጣችሁት አትድኑም" አላቸው:: ወዲያውም ቆፍረው አወጡት::

ቅዱስ ጎርጎርዮስም ድርጣድስና ባለሟሎቹንም ፈወሳቸው:: በዚህም ድርጣድስም አምኖ እህቱን ጨምሮ ከነቤተሰቡ ክርስቲያን ሆነ።

ቅዱስ ድርጣድስም አርማንያም በ301 ዓ.ም. የመጀመሪያዋ የክርስቲያን ሀገር እንድትሆን በአዋጅ አስነገረ። ቅዱስ ጎርጎርዮስንም የአርመን ፓትርያርክ እንዲሆን ፈቀደ። አብያተ ጣዖታትንም አዘግቶ በምትካቸው አብያተ ክርስቲያናትን አሳነጸ።

ቅዱስ ጎርጎርዮስም  ተበትኖ የነበረውን የቅድስት አርሴማንና የሰማዕታቱን አጽም ሰብስቦ ቤተ ክርስቲያን አሳንጾ በታኅሳስ 6 በክብር አፈለሰው። ያሳረፈበት ስፍራም በራዕይ እግዚአብሔር ገልጦለት ነበር።

ከዚህም በኋላ በአርማንያ እየተዟዟረ ወንጌልን እየሰበከ ክርስቲያኖችን ወደ ጌታ በረት ጨመረ። በዚህም ቅዱስ ጎርጎርዮስ ከሳቴ ብርሃን በማለት በአርመኖች ዘንድ ይጠራል።

ቅዱስ ድርጣድስም ስለ እምነትም ከጣዖት አምላኪዎች ጋር ከፍተኛ ትግል አድርጓል። በዚህም በ11ኛው ሰዓት የመጣው ንጉሥ በአርመን ቤተ ክርስቲያን <<ታላቁ ቅዱስ ድርጣድስ ሣልሳዊ|Tiridates III of Armenia >> በማለት የቅድስና ማእረግ ተሰጥቶ በታላቅ ክብር ይዘከራል። የሚታሰበውም በበዓለ ሃምሳ  ከአምስተኛ እሑድ ቀጥሎ ባለው ቅዳሜ ላይ ነው።

ዳግመኛም በዚህ ዕለት ከሰማዕቷ ጋር የመንፈስ እናቷን ቅድስት አጋታን ልናስባት ይገባናል:: ይህች እናት እመ-ምኔት ስትሆን ቅድስት አርሴማን ታስተምራት: ታጸናት: ከጐኗም ትቆምላት ነበር:: ረሃቧን: ጥሟን: ስደቷን: መከራዋንም ሁሉ አብራት ተሳትፋለች:: በፍጻሜውም አብራት ተሰይፋለች።

ከላይ የተጠቀሱትን ታሪኮች መሠረት በማድረግ የሰማዕቷን ቅድስት አርሴማ ሥዕል በሠዓሊ ኃይለማርያም ሽመልስ (@ethioicons @shihaile) ተስሏል። 

የተሣለው ለደብረ ወርቅ ዋዱ ቅድስት ቁስቋም ቤተ ክርስቲያን በ2017ዓ.ም. ነው። አሣሣሉንም ስንመለከት ከቅድስት አርሴማ ጋር በአንድነት  ቅድስት አጋታ እመ ምኔት(ጋያኔ)፣ ማኅበረ ደናግላን ሰማዕት፣ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ፓትርያርክ፣ ቅዱስ ድርጣድስ እና ቅዱስ ራጉኤልን በመጨመር ነው። የሥዕሉ ምስጢር ከስር ቀርቧል።

1. መልአኩ ከላይ መሆኑ ከፍ ያለና ሰማያዊ የሰማዕትነት አክሊልን እንደተቀበለች ለማመልከት ነው። ይህ ደግሞ በጣና ገዳማት መልአኩ ባለበት ስፍራ አክሊል ሲወርድላት ከተሳለው ሥዕል መነሻ በማድረግ የተሣለ ነው።

2. በስተግራ እመ ምኔት ቅድስት አጋታ ክብሯን እንድትጠብቅ ስትነግራት ይታያል። በስንክሳር ላይም የተመዘገበውን ምክሯን በመልእክት መልኩ ይዛ ትታያለች።

3. ከቅድስት አጋታ አጠገብ የእጅ ስራ አብራ የነበረች ደንግል ተስላለች። ይህንን የእጅ ስራ እየሸጡ ለእለት ምግብ ይውሉ እንደነበር ስንክሳሩ እንደሚገልጸው። ይህንንም ለመጠቆም በእጇ ብልቃጥ ይዛ ትታያለች።
በተጨማሪ ሌሎች ደናግል ሰማዕታት አብረው ይታያሉ።

4. በስተቀኝ በኩል ደግሞ ቅዱስ ጎርገርዮስ የፓትርያርክ ቆብ አድርጎና ልብሰ ተክህኖ ለብሶ እና ወንጌልን ይዞ ይታያል። ይህም ወንጌል በሀገረ አርማንያ ያዳረሰ መሆኑን ያጠይቃል።

5. ቅዱስ ድርጣድስ ደግሞ ዘውድ አድርጎ በእጁ ዓለምን ይዞ ይታያል። ይህም ንግሥናውን እና በግዛቱ ወንጌል እንዲስፋፋ ማድረጉን ያመለክታል።
ከእርሱ አጠገብ ያሉት ደግሞ ከአርሴማ ጋር አብረው የነበሩ ወንድ ሰማዕታት ይወክላሉ።

6. ከጀርባ ደግሞ የምንመለከተው ቤተ ክርስቲያን በንጉሥ ድርጣድስ ፈቃድና በቅዱስ ጎርጎርዮስ አማካኝነት የታነጸው ሕንጻን ይወክላል። ይህች ቤተክርስቲያን ደግሞ የቅድስት አርሴማ፣ ቅድስት አጋታና የደናግል ሰማዕታት ቅዱስ አጽም ማረፊያን ትወክላለች።

በአጠቃላይ በስተግራ ሰማዕትነቷን በስተቀኝ ደግሞ ቅዳሴ ቤቷን በማሰብ ተሥሏል። ይህንንም ለመግለጽ አርኬ በቀኝ እና በግራ ተጽፎ ይነበባል።

ምንጭ

* ስንክሳር መስከረም እስከ የካቲት ትንሳኤ ዘጉባኤ
* Wikipedia Tirtades III, Gregory the illuminator
*ዝክረ ቅዱሳን ቴሌግራም ገጽ

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

17 Nov, 18:50


ስለ ሁሉም ነገር የእግዚአብሔር ስም ይመስገን

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

11 Nov, 12:39


አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም እስኪ ገቡ ድረስ ያለውን ታሪካቸውን የሚዘክረውን ቅዱስ ሥዕል እነሆ። እነዚህ ሥዕሎች በብሪቲሽ ሙዝየም የሚገኝ የገድለ ተክለሃይማኖት ያሉ ናቸው።

ትውፊቱን የጠበቁ ቅዱሳት ሥዕላትን ለማግኘት፣ ለመመልከትና ለሌሎች ለማጋራት @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

11 Nov, 12:32


ሦስት ሺ ቤተሰቦች በቴሌግራም ላደረሰን አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
እንደ እግዚአብሔር መልካም ፍቃድ መጪው ዘመን በየዕለቱ ቅዱሳት ሥዕላትን የሚለጠፍበት ጊዜ ያደርግልን።
ኃይለማርያም ሽመልስ።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

07 Nov, 13:59


ስለ ሁሉም ነገር የእግዚአብሔር ስም ይመስገን።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

07 Nov, 13:57


Channel photo updated

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

06 Nov, 08:26


https://ethioicons.wordpress.com/2015/11/07/%e1%88%a0%e1%8b%93%e1%88%8a-%e1%8a%a5%e1%8a%93-%e1%89%85%e1%8b%b1%e1%88%b5-%e1%8a%a0%e1%89%a1%e1%8a%90-%e1%88%98%e1%89%a3%e1%8b%93-%e1%8c%bd%e1%8b%ae%e1%8a%95-%e1%89%b0%e1%8a%ad%e1%88%88-%e1%88%9b/

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

06 Nov, 07:12


እንኳን ለአቡነ መብዓ ጽዮን ዓመታዊ የእረፍት በዓል አደረሳችሁ።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

05 Oct, 09:21


https://youtu.be/Tzq2bTK3OmQ?si=4UnRB9qncerCnNQ_

በወቅታዊ የቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ የተደረገ ቃለ መጠይቅ

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

05 Oct, 08:07


በዲያቆን ሚልኪያስ የተዘጋጀውን ድንቅ animation ስለ ጣፋጩ የጽጌ ወራት እስቲ ተጋበዙልኝ። በማኅበራዊ ትስስር ገብታችሁም ፎሎ አድርጉት አበረታቱት።

በእውነቱ እንዲህ ያለ ስራ ለማየት መነሻ ቢሆንም ያሳኝን እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ።

ከስር የጥበበኛውን ዲያቆን አድራሻ አስቀምጫለሁ ገብታችሁ ተወዳጁት።

ክበበ ጌራ ወርቅ ጽሩይ እምዕንቈ ባሕርይ ዘየኃቱ።
እንኳን ለጾመ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ።

   👇🏾👇🏾👇🏾Social media👇🏾👇🏾👇🏾👇🏾

@milkmalachi

Instagram      Tiktok       You Tube

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

02 Oct, 07:46


https://youtu.be/2WGurCxJw88?si=JbdPXtocGYt-1NzE

በዛሬ ዕለት ከሚታሰቡት ቅዱሳን መካከል የቅዱሳን ሰማዕታትን ዜና መዝግቦ ያቆየ እና የተመኘውን ሰማዕትነት ስለ ክርስቶስ ብሎ የተቀበለው ቅዱስ ዮልዮስ (Julian of Ekfahs) ሲሆን ፊልሙን በግብፅ ቤተ ክርስቲያን የተዘጋጀውን እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ።

ማሳሰቢያ ፊልሙ በአረብኛ ቢሆን ገላጭ እንግሊዝኛ ጽሑፍ ከስር ስላለው እርሱን በማንበብ መከታተል ትችላላችሁ። ግዜውና ጸጋው የታደላችሁ ደግሞ ወደ ሀገራችን ቋንቋ በመተርጎም ለብዙ ሰው እንዲደርስ በወንድማዊ ፍቅር እጠይቃለሁ።

ይህ ስራው ደግሞ የቅዱሳን ሰማዕታትን ለሥዕላቸው መነሻ የሚሆን ታሪክ ምትክ የሌለው ምንጭ በመሆን እያገለገለ ይኖራል።

ስለዚህም ነገር ቤተ ክርስቲያን ስትዘክረው ትኖራለች።

ትውፊቱን የጠበቁ ቅዱሳት ሥዕላት ለመመልከት @ethioicons የቻናላችን ቤተሰብ ይሁኑ።


ሰላም ለዮልዮስ እምኀበ እግዚአብሔር ዘተሠይመ፤
ከመ ያስተጋብአ ዜና አበው ወዘሰማዕታት ዐጽመ፤
እድኅሬሁ ዝንቱ መኮንነ ጥዋ ክሳዶ ገዘመ፤
ሰላም ለኮቶሎስ ወለእኅቱ አዳመ፤
ምስለ ባላን ወጣጦስ ዘገብረ መድምመ!

ምንጭ
ፊልም ከዳር አንቶን ዩትዩብ ገጽ
አርኬ ÷ዝክረ ቅዱሳን - (ርቱዓነ ሃይማኖት)
https://t.me/zikirekdusn

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

21 Sep, 08:22


††† እንኳን ለቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት እና ቅድስት ታኦድራ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት †††

††† በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ቀጥሎ አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ ቅዱስ ፋሲለደስ ነው:: እንዲያውም ለዘመነ ሰማዕታት መሪና አስተማሪ እርሱ ነበር::
እስኪ በጥቂቱ ነገሩን ከሥሩ እንመልከተው::
በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የሮም መንግስት ዓለምን የሚያስተዳድረው በሁለት ከተሞች: ማለትም በራሷ በሮምና በአንጾኪያ ነበር:: የወቅቱ ንጉሥ ኑማርያኖስ ሲሆን የቤተ መንግስቱ ልዑላንና የጦር አለቆች ቅዱሳኑ:- ፋሲለደስ: ገላውዴዎስ: ፊቅጦር: መቃርስ: አባዲር: ቴዎድሮስ (3ቱም): አውሳብዮስ: ዮስጦስ: አቦሊ: ሌሎቹም ነበሩ::

ሴቶቹ ደግሞ ቅዱሳቱ:- ማርታ: ሶፍያ: ኢራኢ: ታኡክልያ: ሌሎቹም ነበሩ:: ለእነዚህ ሁሉ የበላይ ደግሞ ቅዱስ ፋሲለደስ ነበር:: ወቅቱ ከፋርስ: ከቁዝና ከበርበር ጦርነት የሚበዛበት ነበርና ባጋጣሚ ንጉሡ ኑማርያኖስ በሰልፍ መካከል ተመትቶ ወደቀ /ሞተ/::

የሮም መንግስትም ባዶ ሆነች:: ዙፋኑን መያዝ ለቅዱስ ፋሲለደስም ሆነ ለሌሎቹ ቅዱሳን ቀላል ነበር:: ግን እነሱ ዝም ብለው ጠላትን ለመዋጋት ወጡ::

በዘመኑ ደግሞ በግብጽ የፍየል እረኛ የነበረና ከልጅነቱ ሰይጣን የሚያናግረው አንድ አግሪዻዳ የሚሉት ጉልበተኛ ሰው ነበር:: ንጉሡ ከወለዳቸው ልጆች ሁለቱ ሴቶች ክፉዎች ነበሩና ትንሿ አግሪዻዳን ማንም በሌለበት አንግሣ ጠበቀቻቸው:: ስሙንም ዲዮቅልጢያኖስ አለችው::

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሰይጣን ቀጥሎ እንደዚህ የከፋ ስም የለም:: የዓለም ክርስቲያኖችን የጨፈጨፈ ሰው ነው:: ትልቋ ደግሞ የትንሿን አይታ መክስምያኖስ የሚባል አውሬ አግብታ አነገሠችው:: ዓለምም በእነዚህ ጨካኝ ሰዎች እጅ ወደቀች::

ሠራዊቱ ሁሉ በሚሊየን ይቆጠራሉ:: የተደረገውን ሲያዩ ተበሳጩ:: ይህንን የተመለከተው ቅዱሱ ፋሲለደስ ግን ልዑላኑንና አለቆችን ሰብስቦ:- "ይህ ዓለም ከነ ክብሩ ጠፊ ነው:: ስለዚህ የተሻለውን የክርስቶስን መንግስት እንምረጥ" አላቸው:: ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ ደስ ተሰኝተው ምድራዊ ክብራቸውን ሊተው ወሰኑ::

ቀጥለውም በአንድ ቤት ተሰብስበው ይጾሙ: ይጸልዩ ገቡ:: ወደ ውጪ የሚወጡት ለምጽዋት ብቻ ነበር:: ከሃዲውም ይህንን ሲያይ የልብ ልብ ተሰማው:: ከድሮ ያሰበውንና ክርስቲያኖችን የማጥፋቱን እቅድ ሊፈጽም ምክንያት አገኘ::

አባ አጋግዮስ በሚባል መነኩሴ ምክንያት "አብያተ ክርስቲያናት ይትዐጸዋ: አብያተ ጣዖታት ይትረኀዋ-ቤተክርስቲያኖች ይዘጉ: ቤተ ጣዖቶችም ይከፈቱ" አለ:: አዽሎን: አርዳሚስ የሚባሉ ጣዖቶችንም አቆመ::

በዚህ አዋጅ ምክንያትም የክርስቲያኖች ሰቆቃ ጀመረ::
*ምድር በደም ታጠበች::
*ቅዱሳኑ ቀባሪ አጡ::
*እኩሉ ተገደለ: እኩሉ ተቃጠለ: እኩሉ ታሠረ: እኩሉም ተሰደደ:: በዚህ ጊዜ 'መራሔ ትሩፋት' ቅዱስ ፋሲለደስ ለሰማዕትነት ይበቁ ዘንድ ስለ ራሱና ስለ ወገኖቹ ጸለየ::
ቅዱስ ሚካኤልም በግርማ ወርዶ ቅዱሱን ወደ ሰማይ አወጣው:: ከቅዱሳን ጋር በገነት አስተዋውቆት: ክብረ ሰማዕታትን አሳይቶት: ከጌታ ዘንድ አስባርኮት: ከሕይወት ውሃ ምንጭም አጥምቆ መለሰው::ቅዱስ ፋሲለደስም ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ በንጉሡ ፊት ቆመ::

ንጉሡ ፈራ: እርሱ ግን በፈጣሪው ስም መሞት እንደሚፈልግ ነገረው:: ሊያባብለው ሞከረ: አልተሳካም እንጂ:: ከዚያም አስሮ ወደ አፍራቅያ (አፍሪካ) ላከው:: መጽሩስ የሚባል መኮንንም ቅዱሱን አሰቃየው::

እርሱ የሁሉ የበላይ ሲሆን ስለ ክርስቶስ ሁሉን ተወ:: አካሉ እስኪቆራረጥ ገረፉት: በምጣድ ላይ ጠበሱት: አበራዩት: በወፍጮም ፈጩት:: እርሱ ግን በፈጣሪው ታምኗልና ሁሉን ታገሰ:: ሁለት ጊዜ ገድለውት ከሞት ተነሳ:: በተአምራቱ ምክንያትም ከከተማው ሕዝብ ግማሹ ያህል ከአሕዛባዊነት ተመልሶ ሰማዕት ሆነ::

በመጨረሻም በዚህ ዕለት አንገቱን ሲቆርጡት ደምና ወተት ፈሶታል:: መላእክትም እርሱን ለመቀበል ዐየሩን ሞልተውታል:: ከልዑላኑ ወገንም የቅዱስ ፋሲለደስን ሚስትና ልጆችንጨምሮ አንድም የተረፈ የለም:: ሁሉም በሰማዕትነት አልፈዋል::

††† እናታችን ቅድስት ታኦድራ †††

††† ይህች ቅድስት እናታችን የትእግስት እመቤት ናት:: ትእግስቷ: ደግነቷ ፈጽሞ ይደነቃል:: ታሪኳ ደግሞ በሆነ መንገድ ከቅድስት እንባ መሪና ጋር ይገናኛል::

ቅድስት ታኦድራ ግብጻዊት ስትሆን ተወልዳ ያደገችው በእስክንድርያ ነው:: ከሕጻንነቷ ጀምራ ቅን ነበረች:: ምንም እንኳ የምናኔ ሰው ብትሆንም ወላጆቿ ያመጡላትን ባል 'እሺ' ብላ አገባች:: ለተወሰነ ጊዜም በሥጋ ወደሙ ተወስነው ከባሏ ጋር በሥርዓቱ ኖሩ::

ለቤተ ክርስቲያን ከነበራት ፍቅር የተነሳ ጠዋት ማታ ትገሰግስ ነበር:: አንድ ቀን ግን መንገድ ላይ የሆነ ፈተና ጠበቃት::ከረዥም ጊዜ ጀምሮ በመልኳ ምክንያት ለኃጢአት ተግባር ይፈልጋት የነበረ አንድ ጐረምሳ ድንገት ያዛት:: ታገለችው: ግን ከአቅሟ በላይ ነበር:: ጮኸች:የሚሰማትም አልነበረም:: ሰውየው የሚፈልገውን ፈጽሞ: ከክብር አሳንሷት ሔደ:: ይህንን መቻል ለአንዲት ንጽሕት ወጣት ምን ያህል ከባድ እንደ ሆነ መረዳቱ አይከብድም::

እጅግ መጥፎ ሰው: በቀለኛም ለመሆን ከዚህ በላይ ምክንያት አይኖርም:: ቅድስቷ ግን ከወደቀችበት ተነስታ መሪር እንባን አለቀሰች:: ሕመሟን ችላ ወደ ቤቷ ላትመለስ ወደ በርሃ ተጓዘች:: ወደ ገዳም ገብታ በወንድ ስም 'አባ ቴዎድሮስ' ተብላ መነኮሰች:: በአካባቢው የሴቶች ገዳም አልነበረም::

የሚገርመው በገዳም ውስጥ ሆና ያንን ጨካኝ ሰው ይቅር አለችው:: ቀጥላም ስለ እርሱ ኃጢአት ንስሃን ወስዳ ከባዱን ቀኖና ተሸከመችለት:: ይሔ ነው እንግዲህ ሕይወተ ቅዱሳን ማለት: ራስን አሳልፎ ለጠላት መስጠት:: (ዮሐ. 15:13) ፈተናዋ ግን ቀጠለ::

ወንድ መስለዋት 'በአካባቢው ከምትገኝ ሴት ጸንሰሻል' ብለው ከገዳም አባረሯት:: ያልወለደቺውንም ልጅ ታሳድግ ዘንድ ሰጧት:: አሁንም በአኮቴት ተቀብላ ለ7 ዓመታት በደረቅ በርሃ ተሰቃየች:: ልጁንም አሳደገች:: ከዚያም ከባድ ንስሃ ሰጥተው ተቀበሏት:: ቅድስት ታኦድራ እንዲህ ስትጋደል ኑራ በዚህች ቀን ዐርፋለች:: በዕረፍቷም ቀን ክብሯ ተገልጧል::

††† ቸር አምላክ የቅዱሳኑን ትእግስትና መንኖ ጥሪት አይንሳን:: ከበረከታቸውም ያድለን::

††† መስከረም 11 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ፋሲለደስ ሰማዕት
2.ቅድስት ታኦድራ እናታችን
3.ቅዱስ ቆርኔሌዎስ ሐዋርያዊ (ሐዋ. 10ን ያንብቡ)
4.ቅድስት በነፍዝዝ ሰማዕት
5."3ቱ" ገበሬዎች ሰማዕታት (ሱርስ: አጤኬዎስና መስተሐድራ)

=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ያሬድ ካህን
2.ማር ገላውዴዎስ ሰማዕት
3.ብፁዐን ኢያቄምና ሐና
4.አቡነ ሐራ ድንግል ጻድቅ

††† "ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ: ወይስ ጭንቀት: ወይስ ስደት: ወይስ ራብ: ወይስ ራቁትነት: ወይስ ፍርሃት: ወይስ ሰይፍ ነውን? 'ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን:: እንደሚታረዱ በጎች ተቈጠርን' ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው:: በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን::" †††
(ሮሜ. ፰፥፴፭)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

21 Sep, 08:17


እንኳን ለቅዱስ ፈሲለደስ የሰማዕትነት በዓል አደረሳችሁ። እነዚህ ሥዕሎች የሚገኙት በዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ነው።

ኦርቶዶክሳዊ ትውፊትን የጠበቁ ቅዱሳት ሥዕላትን ለመመልከት እና ለማግኘት @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።ይጠቅማል ብለው ካሰቡ ለሌሎች ያጋሩት።

በሠዓሊ ኃይለማርያም ሽመልስ በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ ጥናት አጥኚና ጸሐፊ።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

20 Sep, 06:38


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤፤

መስከረም 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

+" በዓለ ስዕለ አድኅኖ "+

ይህች ቀን በቤተ ክርስቲያን ስለ ቅዱሳት ስዕላት የሚነገርባት ክብርት ቀን ናት:: 'ስዕለ አድኅኖ' ማለት 'እግዚአብሔር በረድኤት የሚገለጥበት: አንድም በቅዱሳኑ አማካኝነት ጸጋ የሚገኝበት: የሚያድን ስዕል' ማለት ነው::

+ስለዚህ ነገር አንዳንዶቹ ሊነቅፉን ይፈልጋሉ:: እኛ ግን ከማን እንደ ተማርነው እናውቃለን:: ከመነሻው እኛ ስዕልን አናመልክም:: ይልቁኑ አምልኮን እንፈጽምበታለን እንጂ:: ስዕልን ለሰው ልጆች የሰጠ ራሱ ባለቤቱ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ ይመሠክራል::

+እንዲያውም የመጀመሪያው ሰዐሊ ራሱ አምላካችን ነው:: አዳምን እንደ መልኩ: በምሳሌው ሲፈጥረው መላእክት የእግዚአብሔርን ምስል አዳም ላይ አይተዋልና:: (ዘፍ. 1:26) ለሙሴም ስዕለ ኪሩብን እንዲስል ያዘዘ ራሱ ነው:: (ዘጸ. 25:22) በዚያም ላይ ሆኖ ሙሴና አሮንን ሲነጋገራቸው ኑሯል::

+በመቅደሰ ሰሎሞንም ተመሳሳይ ነገርን እናገኛለን:: (2ዜና. 7:12, 1ነገ. 9:1) በሐዲስ ኪዳንም ጌታ ስዕለ ኪሩብ ያለበትን መቅደስ ቤቴ (ማቴ. 21:13): የአባቴ ቤት(ዮሐ. 2:16) ሲለው: በቅዱስ ሰውነቱ ሲመስለውም (ዮሐ. 2:21) እንመለከታለን:: ቅዱስ ዻውሎስ ለገላትያ ሰዎች ስለ ስዕለ ስቅለት ሲያስታውሳቸው (ገላ. 3:1): ቅዱስ ዮሐንስም በራዕዩ በደም የተረጨች ልብስ ብሎ ያላትን መተርጉማን ያትታሉ:: (ራዕይ. 19:13)

+በትውፊት ትምሕርት ደግሞ የመጀመሪያው ስዕል በቅዱስ ሚካኤል ክንፍ ላይ የተሳለ ሲሆን ስዕሉም የእመቤታችን ነው:: "ሚካኤል በክነፊሁ ጾራ መንጦላዕተ ደመና ሠወራ" እንዳለ ቅዱስ ያሬድ:: በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአቃርዮስና ለቬሮኒካ (12 ዓመት ደም ይፈሳት ለነበረችው ሴት) መልክአ ገጹን ሠጥቷቸዋል::

('ቬሮኒካ' በላቲን 'ቬሮን-ኢኮን' 'እውነተኛ መልክ' እንደ ማለት ነው)

+ቀጥሎም ዮሐንስ ወንጌላዊ ለጢባርዮስ ቄሣር ስዕለ ስቅለቱን ሲስልለት ቅዱስ ሉቃስ ደግም የእመቤታችን 'ምስለ ፍቁር ወልዳን' ስሏል:: ከዚያም ሲያያዝ ይሔው ከእኛ ደርሷል::

+ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይ በከተሞች አካባቢ ቅርጾች በዝተዋልና ይሔ አላስፈላጊ መዋስ (ያውም ከመናፍቃን) ቢቀር መልካም ነው ባይ ነኝ:: ኋላ ቁጭ ብለው የሰቀሉትን ቁሞ ማውረድ ከባድ ነውና::

+" ጼዴንያ "+

+በዚህች ቀን ቅዱስ ሉቃስ የሳላትና ሥጋን የለበሰችው: ከፊቷም ወዝ የሚወጣትና ድውያንን የምታድነው የድንግል ማርያም ስዕለ አድኅኖ ወደ ጼዴንያ ከወዳጇ ከብጽዕት ማርታ ዘንድ ገብታለች:: ቅድስት ማርታ ሃብት ንብረቷን በአብርሃማዊ ተግባር (በምጽዋትና እንግዳን በመቀበል) ላይ ያዋለች ክብርት ሴት ናት::

+ለእመ ብርሃን ካላት ፍቅር የተነሳ እንቅልፍ አልነበራትም:: ተግታ ታገለግላትም ነበር:: ስዕሏን እንዲያመጣላት የላከችው ኢትዮዽያዊው መነኩሴ አባ ቴዎድሮስ የስዕሏን ተአምራት ባየ ጊዜ ለራሱ ለመውሰድ ሞክሮ ነበር:: (እርሱ ምን ያድርግ! እኔም ብሆን ይህንኑ ነበር የማደርገው)

+ነገር ግን ከሁሉም በተሻለ የምትወዳት ቅድስት ማርታ ነበረችና በድንቅ ተአምር: በዚህች ቀን ወደ ጼዴንያ ገብታለች:: ቅድስት ማርታም ያለ ዕረፍት ስታገለግላት ኑራ ዐርፋለች:: ይህቺ ክብርት ስዕለ አድኅኖ የአሁን መገኛ 4 መረጃዎች አሉ:-

1.ያለችው ኢትዮዽያ ውስጥ (ደብረ ዘመዳ በሚባል ገዳም) ነው:: የመጣችውም ከግማደ መስቀሉ ጋር ነው::
2.ያለችው በቀደመ ቦታዋ ነው::
3.የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ወስደዋታል::
4.በፈጣሪ ጥበብ ተሰውራለች::

+" ልደታ ለማርያም "+

+በግብጽ ውስጥ ከሚገኙ ገዳማት በአንዱ: ማለትም በአስቄጥስ ደብረ አባ መቃርስ የእመቤታችንን ዜና ሕይወት የሚናገር 1 መጽሐፍ አለ:: መጽሐፉ እንደሚለው እመ ብርሃን ድንግል ማርያም የተጸነሰችው ታሕሳስ 17 ቀን ነው:: በዚህ ሒሳብ መሠረት ደግሞ እመ አምላክ የተወለደችው መስከረም 10 ቀን ነው:: ዓለማቀፍ ትውፊቱ ግን ነሐሴ 7 ተጸንሳ: ግንቦት 1 ቀን መወለዷን ያሳያል::

+" ተቀጸል ጽጌ / አጼ መስቀል "+

+'ተቀጸል ጽጌ' ማለት 'መስቀል ሆይ! በአበባ አጊጥ' እንደ ማለት ሲሆን 'አጼ መስቀል' ደግሞ አጼ ገብረ መስቀልን: አንድም አፄ ዳዊት ቀዳማዊን ይመለከታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

+በሃገራችን ኢትዮዽያ የነገረ መስቀሉ ትምሕርት ከመጣ ጀምሮ መስቀል ይከበራል:: በአደበባባይ ግን እንዲከበር ያደረጉት የቅዱስ ካሌብ ልጅ አፄ ገብረ መስቀል ናቸው:: በወቅቱ ንጉሡ: ሠራዊቱ: ዻዻሱና ሕዝቡ በተገኙበት ቅዱስ ያሬድ "መስቀል መልዕልተ ኩሉ ነገር: ያድኅነነ እምጸር-መስቀል ከሁሉ ነገር በላይ ነው: ከጠላትም ያድነናል" እያለ ይዘምር ነበር::

+የአበባ ጉንጉንም ለመስቀሉና ለንጉሡ ይቀርብ ነበር:: ከ800 ዓመታት በሁዋላም አፄ ዳዊት ግማደ መስቀሉን ባስመጡ ጊዜ መስከረም ቀን ተተክሎ ታላቅ በዓልም ሆኖ ተከብሯል::

+" ንግሥተ ሳባ "+

+ይሕቺ ደግ ኢትዮዽያዊት ከ3 ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት:: በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛለች::

+ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች:: ድንግልናዋን ለታላቁ ንጉሥ ሰሎሞን ሰጥታ ምኒልክን ወልዳለች:: ይህቺ ንግሥት በጌታችን (በፈጣሪ) አንደበትም ተመስግናለች:: (ማቴ. 12:42) በስምም "ሳባ: አዜብና ማክዳ ተብላ ትታወቃለች:: ዛሬ ዕለተ ዕረፍቷ ነው::

+እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ጣዕሟን ፍቅሯን: ጸጋ በረከቷን: ከስዕሏም ረድኤት ትክፈለን:: የቅዱሳኑም ክብር አይለየን::

+መስከረም 10 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅድስት ድንግል እግዝእትነ ማርያም
2.በዓለ ስዕለ አድኅኖ
3.ቅዱስ እፀ መስቀል (ተቀጸል ጽጌ)
4.ቅዱስ ሉቃስ ወንጌላዊ
5.ቅድስት ማርታ ዘጼዴንያ
6.ቅድስት ዮዲት ጥበበኛዋ
7.ንግስተ ሳባ / ማክዳ / አዜብ
8.ቅድስት መጥሮንያ ሰማዕት
9.አፄ ዳዊት ንጉሥ
10.ቅድስት አትናስያና 3 ልጆቿ



=>ወርሐዊ በዓላት
1.ቅዱስ ናትናኤል ሐዋርያ
2.ቅዱስ ኒቆላዎስ ዘሃገረ ሜራ
3.አቡነ መልክዐ ክርስቶስ
4.ቅዱስ ያዕቆብ ሐዋርያ (ወልደ እልፍዮስ)
5.ቅድስት ዕሌኒ ንግስት
6.ታላቁ ቅዱስ ቆስጠንጢኖስ

++"+ የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ! በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተስሎ ነበር:: ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው? +"+ (ገላ. 3:1)

‹‹‹‹ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ››››

https://t.me/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

16 Sep, 18:55


https://youtu.be/c1kYAMaLd80?si=vKZTfhY_20f4TZdm

በ20ኛው መ.ክ.ዘ. የነበሩት በፍቅርና በተአምር የተሞሉት የቅዱስ አባ መቃርዮስ ጳጳስ ፊልምን እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ። በጣም ልብን የሚመስጥ እና ሀሴትን የሚመሉ ካወኳቸው እለት ጀምሮ በድካም ውስጥ ብሆንም የማልረሳቸው ፈጥኖ ደራሽ አባት ናቸው ተጠቀሙባቸው።

ማስታወሻ፥ ፊልሙ እንግሊዝኛ ገላጭ ጽሑፍ ያለው በአረብኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ፊልም በመሆኑ እያነበባችሁ ተመልከቱት። አረብኛ አልሰማም ብላችሁ ይህንን ድንቅ ገደል ከማየት እንዳያመልጣችሁ። የአቡነ መቃርዮስ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

16 Sep, 13:59


በሰማእቱ ስም ጸበል እንጂ ቢራ አንጠጣም!
ቅዱስ ጊዮርጊስ የቤተ ክርስቲያናችን ሰማዕት፣ የሕይወታችን አጋር ነው። የሰማእቱ ስም ክቡር፣ ንጹሕ ነው። ሥዕሉ በተቀደሰ ቦታ በቢራ ጠርሙስ አይለጠፍም። ስሙ የድኅነት መንገድ የስካር ማድመቂያ አይለም። በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ጸበል እንጂ ቢራ አንጠጣም።

👇👇👇👇👇👇👇👇
ይህንን ቻሌንጅ ባላችሁ የሚዲያ አማራጭ (በቲክቶክ፣ በዩቱዩብ፣ በፌስቡክ፣ በቴሌግራም፣ በኢንስታግራም)፣ እንዲሁም ለጓደኞቻችሁ ሼር በማድረግ የሰማዕቱን ስም እናስከብር።

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

03 Sep, 06:59


https://youtu.be/Dh1Ssdk5HrM?si=IuQwomPfUKwoJAVz

ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons

01 Sep, 18:59


ሲጠበቅ የነበረው የታዳጊዎች የሥእል አውደ ርእይ ተከፈተ

የሰማይ መስኮቶች በሚል ርእስ በታዳጊ የሰንበት ትምህርት ቤታችን ሰዓሊያን የተዘጋጀው ልዩ የመንፈሳዊ ሥዕላት አውደ ርእይ ብጹእ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምስራቅ ጉራጌና የማረቆ ልዩ ወረዳ ሐገረሥብከት ሊቀጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል በተገኙበት በደማቅ መርሐግብር ተከፍቷል።  በእለቱም የካቴድራላችን አስተዳደሪ ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ኪሮስ ጸጋዬ፣ የካቴድራሉ ዋና ጸሀፊ መጋቤ ሥርዓት እጓለጽዮን ሀብቴ፣የካቴደራላችን የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ይዘንጋው እንዲሁም የደብሩ ካህናትና ዲያቆናት ተገኝተው አውደ ርእዩን አስጀምረዋል።

ብጹእ አቡነ ኤጲፋንዮስ በመክፈቻ ንግግራቸው ለነገይቱ ቤተክርስቲያን የዛሬዎቹን ሕጻናት በጥበብ ማሳደግ የሚገባ መሆኑን ይህንም ለማድረግ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ድርሻ ቀላል የሚባል አለመሆኑን ጠቅሰው። 

ምእመናንም ይህን እስከ ጳጉሜን 3 የሚቆይ አውደ ርእይ  ተገኝተው እንዲሳተፉና የታዳጊ ልጆቻቸውን ፍሬ እንዲመለከቱ አደራ ብለዋል።


                                      የሰማይ መስኮቶች
                                  ከነሃሴ 26 - ጳጉሜን 03

http://youtube.com/@EMislene

3,803

subscribers

410

photos

3

videos