ዮሐንስ ጌታቸው @phronema Channel on Telegram

ዮሐንስ ጌታቸው

@phronema


ርቱዕ ሐልዮ
ጥያቄና አስተያየት ካልዎት ይስጡ!
@tmhrte_tsdk_bot

ዮሐንስ ጌታቸው (Amharic)

ዮሐንስ ጌታቸው በአማርኛ በሚኖረው ተማሪዎችን የተመሰረተ መረጃ ላይ ይገኛል። በተለያዩ ርቱዕ ሐልዮ፣ ጥያቄና አስተያየት አገኘነው፣ ለሚስጥልበት የሚፈላገጥ በትርጉም ማሰል ሊያስከትለው ይችላል። ዮሐንስ ጌታቸው በበል ማለት ሁሉም ስራህን ያሳጣል፣ በእነዚህ መረጃዎች በምንጮችህ ቴሌግራም የእርምጃ ግንኙነት ላይ ያስቀምጣል። በወይም በየተለያዩ ስህተት እንትገናኛለን።

ዮሐንስ ጌታቸው

19 Jan, 16:20


+++++#ወይን_እኮ_የላቸውም#++++++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

የቃና ዘገሊላ ታሪክ ውስጥ አስደናቂ ከኾኑ ክስተቶች ውስጥ አንዱ የወይን ማለቅ ጉዳይ ነው። በእርግጥ ቃና ዘገሊላ ውስጥ የተፈጸመው የሰርግ ጉዳይ ጥልቅ መልእክቶችን የተሸከመ መኾኑ በብዙ የሚብራራ ነው። ታሪኩን በጥልቀት ለመረዳት ግን ወደ ታሪኩ ጥልቀት ውስጥ የምንገባበትን በር ማግኘት አለብን። የዮሐንስን ወንጌል ምሥጢራዊነት ወደ መረዳት ከፍታ እስካልወጣን ድረስ በወንጌሉ ውስጥ የተፈጸሙትን አስደናቂ ክስተቶች በአግባቡ መረዳት አንችልም። ማክሲመስ ተናዛዚው መጽሐፍ ቅዱስን በጥቅሉ በቤተ ክርስቲያን ይመስልና የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለችውን ቅድስተ ቅዱሳን ትመስላለች ይላል። ይህ የሚያመለክተው ወንጌሉ የተሸከመውን ጥልቅ ምሥጢር ነው። እንዲያውም ቀለሜንጦስ ዘእስክንድርያ ሦስቱን ወንጌላት በሥጋ የዮሐንስን ወንጌል ደግሞ በመንፈስ ይመስላል። የሌሎቹ ወንጌላት እስትንፋሳቸው የዮሐንስ ወንጌል ነውና!!

ከዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ የዮሐንስን ወንጌል ለመረዳት ሊቁ ኦሪገን እንዳለው ወደ ጌታ ደረት ጋር ጠጋ ብሎ እንደ ዮሐንስ ከጌታ እመቤታችንን መቀበልን ይጠይቃል። ይህ ኹሉ የሚያመለክተው በወንጌሉ ላይ የተጻፉ ክስተቶችን በችኩልነትና በለብ ለብ ስሜት አልፈን እንዳንሄድና በጥልቀት እንድንመረምር ነው። ሰርግ የተፈጸመባት የገሊላዋ ቃና ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያምን በመያዟ ከሚመጣባት ጉድለት ስትድን እንመለከታለን። ከክርስቶስ ጋር ለምናደርገው ግንኙነት የእመቤታችን ልመና እጅግ አስፈላጊ ነው። እርሷ ቀድማን ጉድለታችንን ባታሰማልን ኖሮ መሽራው ክርስቶስ እንዴት ይቀበለን ነበር!!

@እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከቤተ አይሁድ ወገን ስለ ኾነች የአይሁድን ጉድለት በእጅጉ ታውቀዋለች፤ ስለዚህ የሚጠቅማቸውን ወይን ይሰጣቸው ዘንድ ትለምናለች። በመጽሐፍ እንዲህ ተብሏል “እናንተ ሰካራሞች ንቁ ለመስከርም ወይን የምትጠጡ እናንተ ሁላችሁ! ተድላና ደስታ ከአፋችሁ ጠፍተዋልና አልቅሱ፤ እዘኑም።" ኢዩ 1፥5። በመኾኑም አይሁድ የድኅነትን ደስታ በማጣት በኀዘን ውስጥ ናቸው፤ ይህ ነውና የወይን ማጣት!! ወይን እኮ የላቸውም የድኅነት ደስታ ከደጃቸው ጠፍታለችና ስጣቸው ማለቷ ነበር። በተራው ምድራዊ ወይን ሰክረው የድኅነትን ወይን በማጣት ጨለማ ውስጥ ገብተው ነበርና ጉድለታቸውን የምታውቅ ፈጣኗ እናት ለመነችላቸው።

@ወይን እኮ የላቸውም ርቱዕ እምነት የላቸውም። አኹንም በኦሪታቸው ውስጥ የምትታየውን አንተን ወደ ማወቅ አልመጡምና አይኖቻቸውን ከፍተህ ብርሃነ ወንጌልህን ግለጥላቸው። በጨለማ ውስጥ ያለን ነገር ለማየት የግድ ብርሃን እንዲያስፈልግ በእምነት ጨለማ ውስጥ ያሉትን ወይን ርቱዕ እምነትን ሰጥተህ አድናቸው ማለቷ ነው። ያለ እምነት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም ብሎ ቅዱስ ጳውሎስ እንደ ተናገረው በሐዲስ ኪዳኗ ትክክለኛዋ እምነት በኩል ከእግዚአብሔር ጋር እስካልተገናኘን ድረስ በእርግጥም ወይን እኮ የለንም!!

#እመቤታችን ወይን እኮ የላቸውም ማለቷ ሰዎች ከፈሪሓ እግዚአብሔር በመራቃቸው ምክንያት የደረሱበትን መልከ ጥፉነት ለማመልከትና ከዚያ እንድንፈወስ ለማስደረግ ነው። መዝ 127 “ብፁዐን ኩሎሙ እለ ይፈርሕዎ ለእግዚአብሔር ወለ እለ የሐውሩ በፍናዊሁ። ፍሬ ጻማከ ተሴሰይ፣ ብፁዕ አንተ ወሠናይ ለከ፤ ብእሲትከ ከመ ወይን ሥሙር ውስተ ጽርዓ ቤትከ - እግዚአብሔርን የሚፈሩ ኹሉ የተመሰገኑ ናቸው፣ የድካምህን ዋጋ ትበላለህ፤ ምስጉን ነህ መልካምም ይኾንልሀል፤ ምስትህም በቤትህ ውስጥ እንደ ወይን የተወደደች ናት።" በማለት በብዙ አንቀጽ ጀምሮ በአንድ አንቀጽ ወደ ማውራት ይመጣል። ይህ የሚያመለክተው የክርስቶስንና የእርሱ የኾነችውን ቤተ ክርስቲያን ግንኙነት ነው። በቤትህ እንደ ወይን የተወደደች ናት በማለት የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ውበት ያነሣል። ስለዚህ በፈሪሓ እግዚአብሔር ውስጥ የሚኖሩ የቤተ ክርስቲያን አካሎች የምግባር ውበታቸውን ሳያጡት እንደሚኖሩ፤ ወይን እኮ የላቸውም የተባሉት በዚህ ዓለም ፍልስፍናና ፍቅር የነጎዱትን ነው። የጠፉትን ወደ በረቱ ለመሰብሰብ የተደረገ የፍቅር ጥሪ ነው!!

#ወይን እኮ የላቸውም። ፍቅረ ቢጽ ወፍቅረ እግዚአብሔር የላቸውም። የራሳቸውን ስሜት በመውደድ የሠለጠኑ ናቸውና ወይን ፍቅር የላቸውም!! ወይን ጣዕሟ እንደሚያረካ ነፍሳቸው የምትረካባቸው ቃለ እግዚአብሔር የላቸውም!! ቃልህ ለእግሬ መብራት ለመንገዴ ብርሃን ነው ተብሏል እነርሱ ግን ይህ በአንተ ቃል የመመራት ሐሳብ የላቸውምና በቃልህ የመመራት ኃይልን ሙላባቸው!! እንግዳ ክፉ ፈቃድ ተነሥቶባቸዋልና ይህን ድል የሚያደርጉበትን ወይን ትዕግሥትን ስጣቸው። መናፍቃን ለሚያቀርቡባቸው ጥያቄዎች መልስ ሰጥተው ሰውነታቸውን በእውነት መሠረት ላይ ይገነቡት ዘንድ ወይን ማስተዋል የላቸውምና ማስተዋሉን አድላቸው!

#ወይን ሕገ ወንጌል ናት። በሕገ ወንጌል ወይን ውስጥ ገብተው ይኖሩ ዘንድ ወይን የወንጌል ምሥጢራትን የሚረዱበት ሀብተ ትርጓሜ የላቸውም። በወንጌል ውስጥ የተዘገበው ሰላም ቀድሞ ባለበሳቸው ጥላቻ ምክንያት አልተገኘላቸውምና “ወይን እኮ የላቸውም" ። የሕይወት ወይን አንተን ራስህን በማጣት ሕማም ውስጥ ገብተው ቆስለዋልና አምላክነትህን ገልጠህ አሳያቸው። በሕይወት ውጣ ወረድ ውስጥ የሚገጥማቸውን መከራ በጽናት ይቀበሉ ዘንድ ወይን እኮ የላቸውም። በእርግጥ የእመቤታችን ድምጿ በልጇ ዘንድ ይሰማል። የእኛ ጉድለትም ስለ እርሷ ሲባል ይሟላል። ብቻ እናታችን ቅድስት ኾይ ከመዝሙር ይልቅ ዘፈን ደስ የሚያሰኘንን እኛን ወይን እኮ የላቸውም በይልን!! ጌታ ሆይ ወይን ደምህን ጠጥተን ምሬተ ኃጢአታችንን ታስወግድ ዘንድ ስለ እናትህ ብለህ ወይንህን ስጠን! አሜን።

ዮሐንስ ጌታቸው

18 Jan, 19:09


በዓለ ጥምቀት (Epiphany-ኤጲፋኒ)

በዓለ ጥምቀት የመገለጥ በዓል (Feast of Epiphany) እየተባለ ይጠራል። ይህን በዓል የመገለጥ በዓል ያሰኘው በአንድ በኲል ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ወልደ አምላክ መኾኑን አብ በደመና ኾኖ መመስከሩና "ባሕር አየየች ሸሸችም" የተባለው ትንቢት በእርሱ ጥምቀት የሚፈጸም መኾኑ የተረጋገጠበት በመኾኑ ሲኾን በሌላ በኩል የቅድስት ሥላሴ ልዩ አካላዊ ሦስትነት አብ በደመና ኾኖ "የምወደው ልጄ እርሱ ነው፥ እርሱን ስሙት" በማለት መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በመገለጥ የታወቀበት በመኾኑ ነው። በእርግጥ የመገለጥ በዓል እየተባለ የሚከበረው የጥምቀት በዓል ብቻ ሳይኾን የጌታችን የልደት በዓልም ነው። ከቅድስት ድንግል ማርያም በመወለዱ አካላዊ ቃል ሥግው ኾኖ (Incarnated Word Of God) ተገልጿልና። "የዲያብሎስን ሥራ ያፈርስ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ" እንዲል። በጥንቱ ትውፊት መሠረት በዓለ ጥምቀትና በዓለ ልደት በአንድነት በአንድ ዕለት እስከ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድረስ ይከበሩ ነበር። ከአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ ግን በተለያዩ ዕለታት መከበር ጀምረዋል። (Encyclopedia of Religion and Ethics, vol. 3, p. 603)።

ጌታችንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም የኾነ ትሕትናውን ከገለጠባቸው በዓላት መካከል አንዱ ይህ የጥምቀት በዓል ነው። አካላዊ ቃል በባሕርያዊ ተዋሕዶ ሰውነትን ለራሱ ገንዘብ አድርጎ ሥግው ኾኖ ተገልጿል። ፈቃዳችንን በማይገባ ተጠቅመን ከተሰጠን ልዕልና ስንወርድ እግዚአብሔር ቃል ሰው ኾኖ ያድነን ዘንድ በከብቶች በረት በቤተልሔም ተወለደልን። በልደቱ እንደ ገና ልንወለድ የሚገባን ልደት እንዳለ አመለከተን። ይኸውም እርሱ ረቂቅ ሲኾን የእኛን ሰውነት በተዋሕዶ ገንዘብ በማድረግ በሥጋ ግዙፍ ልደትን በመወለድ እኛን ደግሞ በጥምቀት አማካኝነት ረቂቅ ልደት ተወልደን ልጆቹ እንኾን ዘንድ አደለን።

በዓለ ጥምቀትን ስናስብ ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ከወደቅንበት ትዕቢት ተላቀን ወደ ትሕትና እንድንገባ የሚያደርግ አማናዊ ምሳሌ እንዳስቀመጠልን ልብ እንላለን። ይኸውም እርሱ አምላክ ሲኾን ሳለ ምንም የሚይሻው ነገር ሳይኖር በፍጹም ትሕትና በባሪያው በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከመሄድ በላይ ምን ትሕትና አለ! ለአምላክ በከብት በረት ከመወለድ፣ በባሪያ እጅ ከመጠመቅ በላይ ምን ትሕትና አለ! እንግዲህ ይህን የሚረዳ ሰው ራሱን ሰይጣንን ከሚያስመስል ትዕቢት አላቆ በፍጹም ትሕትና አጽር ቅጽር ውስጥ ሊያኖር ይጥራል። በዓለ ጥምቀት የትሕትና ጣዕም የሚቀመስባት ልዩ በዓል ናትና።

የጥምቀት በዓል የብርሃን በዓል (Feast of Light) እየተባለ ይጠራል። ምክንያቱም በጥምቀት አብርኾትን ገንዘብ እናደርጋለንና። (https://saintgeorgechurch.org.au/article/the-feast-of-the-epiphany/)። በዓሉ በዓለ ብርሃን መኾኑን ከተረዳን በበዓሉ ዕለት ብሩህ ሥራ ልንሠራበት ይገባል። ወደ ጨለማ ከሚወስድ የኃጢአት መንገድ ራሳችንን በመጠበቅ፥ ከሥጋዊነትና የግል ስሜትን ከማርካት በመቆጠብ ልናከብር ይገባል። ውድ ወንድም እኅቶቻችን ሆይ! የሕይወት ብርሃን የኾነውን ክርስቶስን የምንለብስበትን ጥምቀት የምናስብበትን በዓል እግዚአብሔር የማይፈቅደውን ነገር በማድረግ ልናከብር ይገባልን? እርሱስ አምላካችን አያዝንብንምን? ስለ እኛ የተደረገውን ነገርስ ማቅለል አይኾንብንምን? ስለዚህ ልቡናችንን ወደ እግዚአብሔር ፈቃድ በመውሰድ ብሩህ በማድረግ ለማክበር ራሳችንን እናዘጋጅ።

የጥምቀትን በዓል የምናከብረው በረከት ለማግኘት መኾኑ እንደ ተጠበቀ ኾኖ ሥግው ቃል ስለ እኛ ያደረገልልን የአርአያነት ሥራ ኹሉ ለመከተል እርሱንም መንገድ አድርገን የድኅነትን ጉዞ ለመፈጸም ነው። ለርሱ ጥምቀት የሚያስፈልገው ሳይኾን መጠመቁም እንድንጠመቅ በሩን ለመክፈት ነውና። የጥምቀትን በዓል የምናከብርበትን ምክንያት አቡነ ጎርጎርዮስ ሲያስረዱ፦ "... የጠበሉን መረጨት አይተው በቀድሞ ዘመን ወደ ሀገራችን መጥተው የነበሩ ኢየሱስሳውያን፣ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በያመቱ ታጠምቃለች ብለው አጥላልተው ጽፈዋል። ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በያመቱ ይህን የምትፈጽመው ጌታችን ለእኛ ብሎ ያሳየውን ትሕትና ለመመስከር፣ ለምእመናን የጌታን በረከተ ጥምቀት ለማሳተም እንጂ የተጠመቁትን ምእመናን እየመላለሰች በየዓመቱ አታጠምቅም። ጥምቀት አሐቲ መኾኗን ታውቃለችና።" ይላሉ። (ጎርጎርዮስ (ሊቀ ጳጳስ)፣ የኢትዮጵያ ኦ/ተ ቤ/ ታሪክ፣ ገጽ 110-111)። መልካም በዓል ይኹንላችሁ።

ዮሐንስ ጌታቸው

17 Jan, 17:43


#የትኛይቱ_ከተራ_ውስጥ_ናችሁ?#

ጥር ዐሥር ቀን የበዓለ ጥምቀት መግቢያ በር ነው። አጽር ቅጽር ይላሏ ከተራ ነውና። ከተራ በአንድ በኩል የወራጅ ውኃን ማቆም፥ መሰብሰብ፥ በአንድ ቦታ ማድረግን የሚያመለከት ሲኾን፥ በሌላ በኩል የእግዚአብሔር ታቦታትን ካህናትና ምእመናን ከትረው (ከበው) መጓዝን ያመለክታል። ይህን ስናስብ ክርስትና አጽር ቅጽር ያለው፥ የተለካ ሕግና ሥርዓት ያለው ርቱዕ ሃይማኖት መኾኑን በከተራ በኩል ልብ ይሏል። ልክ የዓሣ መኖሪያው ውኃ እንደ ኾነ ኹሉ የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆችም ሕይወት ውኃ በኾነው የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮና ሕግ ላይ የተመሠረተ ነው። በእርሷ ሕግና ሥርዓት ውስጥ የማይኖር ከእርሷ ከተራ ውጭ ነው የሚኾነው። የውኃ ዳር አካባቢ የእግዚአብሔር ማደሪያ የኾኑ ታቦታቱ በካህና አማካኝነት የሚጓዙት በውኃ ዳር አካባቢ እንድንተከል ለማድረግ ነው። ይኸውም በቃለ እግዚአብሔር መሠረት ላይ መተከል ነው። በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአስተምህሮ ውኃ አካባቢ እንድንጸና ሊያመላክቱን ውኃ ወዳለበት እንደሚወስዱን አድርገን ብንረዳ እንዴት ያምር! በእርግጥም እንዲያ ነውና።

በወንጌል ትምህርት ያልተከተረ ልቡና ኹል ጊዜም ቢኾን ሲነዋወጽና፥ ወጪ ገቢው ሲያቆሳስለው ይኖራልና። ወንጌል ርቱዕ ሕግ ነው። በጽኑዓን ልቡና ይከተራል። ንጹሐን ቅዱሳን በሕይወታቸው ውስጥ ወንጌልን ከትረው ከዚህ ዓለም ርካሽ አስተሳሰብ ተጠብቀው ኖረዋል። እንግዲያውስ ኹል ጊዜ በዓለ ከተራን ሳናሳልፍ ልንኖርበት ይገባናል። ይኸውም በወንጌል ከተራ ልቡናችንን ሰብስበን መኖር ነው። ሰሎሞን በመኃልየ መኃልይ "የታተመች፣ የዘጋች፣ የተቈለፈች" ገነት ብሎ የሚላት የእኛን ሰውነት ጭምር ነው። በንጽሕናና ሕግጋተ እግዚአብሔርን በመፈጸም አሸብርቃና አምራ ገነት የመሰለች ሰውነት ይሏል የእውነተኛ ክርስቲያን ሰውነት ናት። ተንቀሳቃሽ ከተራዎች ይሏል በቅድስና የቅዱሳንን ሕይወት እየጠጣች የተከተረች የክርስቲያኖች ሰውነት ናት።

ተአምራት ገድላት የእኛን ሰውነት ከተራነት የሚያጸኑ አዕማዳት እንጂ ባልተከተሩ ሰዎች (ኦርቶዶክሳዊ አረዳድ የሌላቸው) የሚፈርሱ ተራ ድርሰቶች አይደሉም። በክርስቶስ አምላክነት አምነን በቅድስና ከተራ ውስጥ ስንኾን እኛ ራሱ ገድልና ተአምር ወደ መኾን ልንሻገር የምንችል መኾናችንን ልብ ልንል ይገባናል። የተአምራትና ገድላት አንዱም ዓላማ ከውጭ ማስቀረት ሳይኾን እኛን ራሱ ማሳተፍና ማለምለም ነውና። የቅዱሳን አበው ርቱዕ የኾነ የሃይማኖት አረዳድ ሲኖረን ያኔ ተንቀሳቃሽ ተአምራትና ገድላት ይሏል እኛው ነን። ለዓሣ በየብስ መኖር ባዕድ እንደ ኾኑ ኹሉ ለክርስቲያን ከተአምራትና ከገድላት መንፈስ ውጭ ኾኖ መኖር ባዕድ ነው። ቅዱሳን አባቶቻችን የከተሩልንን የተአምራትና የገድላትን ከተራ ትተን አሳቾች በግል ስሜታቸው ወደ ሠሯት፥ "የማትከበር ከተራ" እንዳንጓዝ እንጠንቀቅ። የመቅበዝበዛችን ዋና ምክንያትስ የኃጢአትን ጣዕም በውስጣችን ጥልቅ አጣፍጠን መክተራችን አይደለምን? እንግዲህ ከክፉ የኃጢአትና ያለማስተዋል ከተራ እንውጣና ወደ እውነተኛው የከተራ አከባበር እንምጣ!

ከተራ በልቡናችን ውስጥ በንጽሕና መከተሩን የምንረዳው ከአከባበር መንፈሳችን ነው። በዓሉ የጌታችን ጥምቀት መግቢያ ኾኖ ሳለ የዘፈንና የጭፈራ መግቢያ፥ ወዲህም የስካር መግቢያ ካደረግነው ከተራችን ወዴት አለ? ጌታችን በወንጌል በበሩ የማይገባ ሌባና ወንበዴ ነው ማለቱን ልብ እንበል። ወደ ጥምቀት አበው በሠሩልን የከተራ አከባበር በር ካልገባን የጌታ ቃል በእኛ የሚፈጸም ወደ መኾን የሚመጣ መኾኑን ልብ ልንል ይገባል። ሌብነትና ውንብድና ግን በእውነቱ መግቢያ የኾነ አይመስላችሁምን? እስኪ የየሪሳችንን የከተራ አከባበር እንመርምረው! በዓሉን ስናከብረው ምንድን ነው የሚሰማን? ለምንስ ነው የምንሄደው? ምንስ ነው የሚያስደስተን? ዓለምስ በአከባበር ሂደታችን በእርግጥም የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አማናዊ አከባበር እያየች ነውን? እኛ ሌላ አከባበር ፈጥረን ያሰናከልናቸውን ስንት ናቸው? ታቦታቱ ምድርን እየባረኩ ሲዞሩ ያልተነካና ያልተቀደሰ ሐሳብ ያለን ብዙ አይደለንምን? እንግዲያውስ በየግላችን ከሠራናቸው የኃጢአት ከተራዎች እንውጣ። እግዚአብሔር አብ እርሱን ስሙት ባለው ቃል መሠረት ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስን "እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ" ሲል እንስማው። በፍቅር ከተራ ውስጥ ኹሌም ጸንተን ለመኖር እንትጋ! እግዚአብሔር በከተራት አማናዊት ከተራ ውስጥ ልቡናችን ይገባ ዘንድ ኃይሉን ያድለን፤ መልካም በዓለ ከተራ !

ዮሐንስ ጌታቸው

15 Jan, 17:10


#አምላክ_ሰው_ከኾነ_በሰውነት_ያለ_እድፈት_አርፎበታል_ያሰኛል_አምላክ_በቃሉ_ተናግሮ_ብቻ_ማዳን_እየቻለ_ሰው_ኾነ_መባሉ_ተገቢ_አይደለም_ለሚሉና ተያያዥ ጉዳዮች የተብራራበት

#ለብዙዎች_እንዲደርስ_ለሚያውቁት_ይላኩ_ይከታተሉትም_ዘንድ_ተጋብዘዋል!


https://youtu.be/B162zjdniog?si=otXcszpAQ7YpZ3gQ

ዮሐንስ ጌታቸው

15 Jan, 05:49


+++###የሰናዖር_ግንብ###+++

በኦሪት ዘፍ 11፥1 ጀምሮ ስናነብ "ምድር ኹሉ በአንድ ቋንቋና በአንድ ንግግር ነበረች።" በማለት ይጀምራል። ያለምንም መለያየት ዓለም በሙሉ በአንድ ቋንቋ ይነጋገሩ የነበረበትን ዘመን ማሰብ በጣም ጥሩ የሚኾነው ያን ከልቡ አምኖ ለሚሰማውና ለሚያነበው ሰው ኹሉ ነው። ምናልባት አኹን ላይ የአብዛኛዎቻችን አስተሳሰብ በአንዳንድ ሰዎች የሐሳብ መርዝ ስለ ተመረዘ የመጀመሪያው ቋንቋ ኦሮምኛ ወይም አማርኛ፣ ትግርኛ ወይም ጉራግኛ፣ ወላይትኛ ወይም ሲዳምኛ እየተባለ ጭቅጭቅ እንዳይነሣ አስጊ ነው። ሰውን የሚያህል ታላቅ ፍጥረት "ቋንቋ" የተባለ ከመግባቢያነት ያለፈ ነገር የሌለው ነገር ጨፍልቆ እንደ ባርያ መግዛቱ እጅግ በጣም አሳዛኝ ነው። በእርግጥ ቀደምት ሊቃውንትም ይህ የመጀመሪያው ቋንቋ ምን እንደ ኾነ ቁር'ጥ ያለ መልስ አላስቀመጡልንም።

ሊቁ አውግስጢኖስ ዕብራይስጥ የመጀመሪያው ቋንቋ እንደ ኾነ ይናገራል። ዕብራይስጥ ነው የሚሉ ሊቃውንት የሚያነሱት መከራከርያ አዳም፣ ሔዋን፣ ኤደን... የሚሉ ቃላቶች ዕብራይስጥ ስለ ኾኑ ነው። አንዳንዶች ደግሞ ሱርስት ነው ሲሉ ከእኛ ሊቃውንት ደግሞ ግእዝ የመጀመሪያው ቋንቋ እንደ ኾነ አብራርተው ያስረዳሉ። እንግዲህ ይህ ነገር የተለያየ ምልከታ መኖሩን እንድንረዳ ያመለክተናል። መጽሐፍ ቅዱስ አንድ ቋንቋ ብሎ የተናገረው ፍቅር ነው የሚሉ ሊቃውንትም አሉ። በእርግጥ ፍቅር ጣዕም ያለውና ልዩ መግባቢያ ነው። የተፈጠርነውም ኾነ ልንኖር የሚገባን ስለ ፍቅር ነው። ፍቅር የሕይወት ግቢና ትርጒም ነው። በእግዚአብሔር ዘንድ ያለው የአካል ሦስትነት ከባሕርይ አንድነት የተስማማው በፍቅር ነው። ይህን በእንዲህ እናቆየውና የሰናዖር ሰዎች የጀመሩትን የክፋት ሥራ እንዳይሠሩት ያደረጋቸው የቋንቋቸው መደባለቅ ነው። ይህ የቋንቋ መደባለቅ ነገር ወደ ልባቸው እንዲመለሱ ሕያው ማንቂያ ቢኾንም አልተጠቀሙበትም ነበር።

ልባችን በኃጢአትና በክሕደት ሲሞላ የሰናዖር ሰዎችን የሚመስል የክፋት ግንብን ለመገንባት ብቻ እንጂ ለእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ቦታ የማንሰጥ እንኾናለን። እግዚአብሔር በአንድነት ያለመለያየት እንድናመልከው ሲፈልግ እኛ ግን አንድ የሚያደርገንን አምላክ በአንዲት የክፋት ግንብ ላይ ተመሥርተን የምናጠፋው እስኪመስል ድረስ እናምጻለን። አኹን እያየን ያለነው እውነታ ይህን ይመስላል። አማራውም ኾነ ኦሮሞው፣ ወላይታውም ኾነ ሲዳሞው፣ ጉራጌውም ኾነ ስልጤው በዘረኝነት ጎጥ ውስጥ ለመሸሸግ የሰናዖርን ግንብ ለመገንባት ይሯሯጣል። ምንም ዓይነት የክፋት ጦር ቢኖረን አንድ ኾነን ፍቅርን የሚያጠፋ የክፋት ፎቅ መሥራት አንችልም። አንድ ነን ስንል አንድነታችንን እናጣለን። ለዚህም ነው አንድ ነን የሚለው ዕሳቤ ጠፍቶ አርሲ፣ ሰላሌ፣ ሸዋ፣ ጎጃሜ፣ ጎንደሬ፣ ወሎዬና የመሳሰሉት እየተባባሉ መከፋፈል የመጣው። አማራው ብቻውን ያለ ኦሮሞው አያምርም፤ ኦሮሞውም ያለ ወላይታና ጉራጌው አያምርም፤ ትግራዩም ያለ አማራው ምን ውበት አለው?! ውበት እነዚህ ኹሉ በአንድነት ሲሰላሰሉ የሚገኝ ልዩ ኃይል ነገር ነው።

የሰናዖርን ግንብ ለመገንባት በተነሣሱት ሰዎች ላይ የተደረገው የቋንቋ መከፋፈል ጉዳይ ለእነርሱ ጠቃሚ እንደ ነበረ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ያስረዳናል። ምክንያቱም እግዚአብሔር ቸር ስለ ኾነ ከተሳሳቱበት መንገድ እንዲወጡ ያደረገው ተአምራዊ ነገር ነውና። ”በድሮ ጊዜ የተደረገው የቋንቋ መደባለቅ የሚመሰገን ነው፤ ሰዎች ኹሉ በእርጉምነትና በእምነት አልባነት ወደ አንድነት መጥተው ግንብ በመገንባት አደጋን ለመፈጸም ፈልገው ነበርና። ቋንቋቸውን በመደባለቅ የአንድነት ሐሳባቸው ተሰበረ፤ ውጥናቸውም ጠፋ። አኹን የተደረገላቸው ተአምራዊ ነገር አጅግ በጣም ምስጋና የተገባው ነው። ከአንድ መንፈስ በተለያዩ ሰዎች ላይ በመፍሰስ ወደ አንድነት ሥርዓት እንደገና አመጣቸው። የተለያዩ ጸጋዎች አሉ፤ በፍላጎት ላይ የተመሠረቱ ናቸው፥ ኾኖም የተሻለውን የመለየት ጸጋም አለ፤ ኹሉም ምስጋና የተገባቸው ናቸው።" St. Gregory Nazianzen, Oration on Pentecost።

ሰብአ ባቢሎን ያፈራረሱትን የመልካምነት ሐሳብ አምላክ ሰው ኾኖ መጥቶ አራቀው። በሐዋርያትም ልብ የአንድነትን ችግኝ ተከለ፤ እነርሱም ሕያዋን ችግኞች ስለ ነበሩ በዓለም ኹሉ ዞረው በክፋት እሾህ ልባቸው ተወጎቶ የሚደማባቸውን የዚህ ዓለም ሰዎች እሾሃቸውን ነቃቅለው ጥለው ክርስቶስ የተከለባቸውን የፍቅር ችግኝ በሰሚዎቻቸው ጆሮ በኩል ከትተው በልባቸው ውስጥ ተከሉት። የእኛ ጭካኔ የእግዚአብሔርን ፍቅር እንዳናይ ከማድረጉም አልፎ እርሱን ጨካኝ አድርጎ እስከማሳሰብ አድርሶናል። ይህን ኹሉ ለማጠብና ንጹሕ የሐዋርያት ትምህርት የሚዘራበት ልብ ለመያዝ ከተጋን በእርግጥ ከሰናዖር ግንብ ለማምለጥ ዕድሉ ይኖረናል።

ሊቁ አውግስጢኖስ ባቢሎናውያን እግዚአብሔር የሰጣቸውን የፍቅርና የአንድነት ቋንቋ (Language of love and unity) በትዕቢታቸው ምክንያት አጡት ይላል። አንዱን እግዚአብሔርን በተሰጣቸው አንዲት የፍቅር ቋንቋ ማክበር ሲገባቸው ጠሉት። እርሱ በፍቅርና በምሕረት እጁን ዘርጎቶ ሲመጣ እነርሱ በትዕቢት ከእርሱ ርቀው ይሄዳሉ። በትዕቢት ሳጥናኤል ሰይጣን ወደ መኾን ወርዷል። በትዕቢት ቃየል የመጀመሪያ ገዳይ ተብሏሎ። በትዕቢት አይሁድ ከክርስቶስ ይልቅ በርባንን መርጠዋል። ትዕቢት ዐይነ ልቡናን ታጨልማለች። እግዚአብሔርን እንዳናገኝና በረከተ ሥጋ ወነፍስ እንዳይሰጠን መጋረጃ ትኾናለች። ቅዱስ ይስሐቅ ዘሶርያ "ከንቱ ክብርን ሽሽ ትከብራለህና፤ ትዕቢትን ፍራ ከፍ ያልህና የጎላህ ትኾናለህና" በማለት ትዕቢት አስፈሪ ነገር መኾኗን ይነግረናል "Ascetical Homilies" (Homily Five)።

ከላይ ከተገለጸው በተጨማሪ ይስሐቅ ዘሶርያ እንዲህ ይላል፦ ትዕቢት በጨለምተኝነት ጨለምተኛ አድርጎ የሚያስጉዝና የጥበብን ነገር እንዳናይ የሚያደርግ አደገኛ በሽታ ነው። በዚህም ምክንያት በራሱ የጨለማ ሐሳብ ከኹሉ በላይ ራሱን ከፍ ያደርጋል፤ ነገር ግን በጣም ዝቅ ያለና ከማንም በጣም የደከመ ነው። የጌታንም መንገድ ለመማር የማይችል ነው። ጌታም ፈቃዱን ከእርሱ ይሰውራል ምክንያቱም በእርሱ መንገድ ላይ ለመጓዝ ትሕትና የለውምና በማለት የበለጠ ዘርዘር አድርጎ ስለ ትዕቢተኛ ሰው ትዕቢት ይነግረናል St. Isaac the Syrian - "Ascetical Homilies" (Homily Nineteen)።

ትዕቢት ከፍ የሚያደርግ ሊመስል ይችላል እንጂ ፈጽሞ ወደ ድቅድቅ ውስጥ የሚጥል የሰይጣን የመጀመሪያ ተግባሩ ነው። ዮሐንስ ዘሰዋሰው "መላእክት (የአኹኖቹ አጋንንት) ከሰማይ የወደቁ ከትዕቢት ውጭ በኾነ ስሜት አይደለም" በማለት ትዕቢት ከሰማያዊ ክብር የሚወረውር ክፉ ኃይል መኾኑን ያስገነዝበናል St. John Climacus - The Ladder of Divine Ascent (Step 23, Section 12)። የሰናዖርን ግንብ ይሠሩ የነበሩት ሰዎችም የተያዙት በዚህ ጽኑ ሕማም ነው። በትዕቢት ሰማይን የሚነካ ግንብ እንገነባለን ብለው ያስባሉ እንጂ፥ በልባቸው ውስጥ የተገነባው የትዕቢት ግንብ ሰማይ ደርሶ እግዚአብሔርን እንዳስቆጣ አልተረዱም፤ ምክንያቱም ትዕቢታቸው የልቡናቸውን የብርሃን ዓይን አጨልሞባቸዋልና። በሐሳባችን ውስጥ ያስቀመጥነውን ረቂቅ የሰናዖር ግንብ ማፍረስ የሚቻለው እንደ ሐዋርያት ትሕትናንን ገንዘብ ስናደርግ ነው። ሊቁ አውግስጢኖስ በትዕቢት የገባውን የቋንቋ መለያየት በትሕትና አጥፍተው አንድ አደረጉት ይለናል።

ዮሐንስ ጌታቸው

15 Jan, 05:49


ለዚህም ነው ሐዋርያት በተለያየ ቋንቋ የሚናገሩትን በቋንቋቸው ተናግረው ወደ አንድ የመግባቢያ ቋንቋ ወደ ተባለው ወንጌል የሰበሰቧቸው። በወንጌል የሚያምኑ ሰዎች ቋንቋቸው አንድ ነው እርሱም ሰማያዊውን ምስጋና በወንጌል ውስጥ ላገኙት አምላክ በአንድነት ማቅረብ ነው።

አንድ ቲኪኾን የተባለ ሊቅ "ትዕቢት እየሸሸ ሲሄድ ትሕትና መኖር ይጀምራል። ትዕቢት በጣም እየጠፋ ሲሄድ ትሕትና በጣም እያደገ ይመጣል። አንዱ ለሌላኛው በተቃራኒው መንገዱን ይለቃል። ጨለማ ይለያል ብርሃን ይገለጣል፤ ትዕቢት ጨለማ ነው፤ ነገር ግን ትሕትና ብርሃን ነው።" በማለት ከትዕቢት ስንርቅ ከትሕትና ጋር እንደምንገናኝ አመልክቶናል St. Tikhon of Zadonsk - "Journey to Heaven"። እንግዲህ የሰናዖር ግንብ ማለት የሚገነባው ግንብ ብቻ ሳይኾን የማይታየውንም ረቂቅ የትዕቢት ግንብ አመልካች ነው።

"እግዚአብሔርም የአዳም ልጆች የሠሩትን ከተማና ግንብ ለማየት ወረደ።" ይላል። በእርግጥ እግዚአብሔር አንድን ነገር ለማየት እንደ እኛ የቦታ ውስንነት ኖሮበት የሚታየው ነገር ወዳለበት አካባቢ ይሄዳል ለማለት አይደለም፤ ኹሉን የሚያይ አምላክ ሰዎች በፈጸሙት ድርጊት አለመደሰቱን ለማስረዳትና የእኛንም ትኩረት የሰናዖር ሰዎች ወደ ፈጸሙት የድፍረትና የትዕቢት ሥራ አድርጎ ከዚያ ዓይነት ግብር እንድንቆጠብ ሊመክረን ነው። ይህን ታሪክ ያጻፈው እኛን ከእንደዛ ዓይነት ስሕተት ለመጠበቅም ጭምር ነው። ሰው አንድን ነገር ለማየት ከሚታየው ነገር ውጭ መኾን አለበት። ይህም ማለት የሚያየውና የሚታየው ነገር በተለያየ ቦታ መኾን አለባቸው። እግዚአብሔር ግን በኹሉም ቦታ ኾኖ ኹሉንም ያያል፤ ለማየት የማያስችል ምንም ከልካይ ነገር የለውም። በመኾኑም "ለማየት ወረደ" የሚለውን የምናነብ እኛ አንደኛ ቸርነቱን ማድነቅና እያየ ያለየ እስኪመስል ድረስ የሚያፈቅረን አምላክ እንዴት መሐሪ ነው! ብለን እንድናደንቅ ያደርገናል። ኹለተኛ "ለማየት ወረደ" ሲል የእኛን መመለስ ምን ያህል እንደሚሻና ያንም መሻቱን እንድንረዳ ለማድረግ በቋንቋ የማይወሰነው በቋንቋ የተወሰነ እስኪመስል ድረስ ዝቅ ብሎ ማናገሩንም የሚያመለክት ነው።

ተወዳጆች ሆይ! ምናልባት በኃጢአት የሠራነውን የሰናዖርን ግንብ ለማየት እግዚአብሔር ወረድ ብሎ ይኾንን? እንግዲያውስ ወዲያውኑ ይህን ክፉ ሕንጻ እናፍርሰውና የትሕትናንን ሕንጻ ገንብተን አምላካችንን ደስ ለማሰኘት እንፋጠን! "እግዚአብሔርም አለ፦ እነኾ እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፥ ለኹሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ ይህንም ለማድረግ ጀመሩ፤ አኹንም ያሰቡትን ኹሉ ለመሥራት አይከለከሉም። ኑ እንውረድ አንዱ የአንዱን ቋንቋ እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው።" እግዚአብሔር አንዲት የምታደርግ የፍቅር ቋንቋ ሰጥቶ ይሰበስባቸዋል እነርሱ ግን የሚከፋፍል ሥራ ሲሠሩ ይገኛሉ። አንድነትን እንደ ዘመኑ ሰዎች አይሹም። ዛሬ ላይ ብዙ ሰናዖራዊ ሥራ በመሥራት ሕዝባችን ተከፋፍሏል። ስምምነቱን አጥቶ መለያየትን መርጦ በጣም በጭንቅ ውስጥ ገብቷል።

እንግዲህ ብዙዎች የራሳቸውን ቋንቋ ብቻ እንዲነገር ለማድረግ ሲሉ ብቻ ሌሎችን ይገድላሉ፤ በእሳት ያቃጥላሉ፣ በስለት ይቆርጣሉ፤ ይህ እንግዲህ የሰናዖር ግንብ ነው። ወንድም ወንድሙን ጨክኖ ከመግደል የበለጠ ምን በደል አለ? ገዳዮቹ ከገደሉ በኋላም አለመጸጸታቸው ደግሞ የበለጠ የጭካኔያቸውን ደረጃ ያሳያል። የሚሠሩትን የክፋት ሥራ በአንዲት ሰከንድ ማስቆምና እነርሱንም ማጥፋት የሚችለው አምላክ፥ እነርሱን ከማጥፋት ይልቅ ሥራቸውን ለማስቆም ቋንቋቸውን ደባለቀው። የቋንቋቸው አንድነት ጠፋ፤ እርስ በእርሳቸው በንግግራቸው ተለያዩ፤ አኹንም ግን ጥፋታቸውን ወደ መረዳት አልመጡም። ይህ የሚያመለክተው የቅድስት ሥላሴን ይቅርባይነትና ቻይነት ነው። አብ ወልድንና መንፈስ ቅዱስን "ኑ" ይላቸዋል። በቅድስት ሥላሴ አንዲት ይቅርባይነት የምንድን መኾኑን ለማስረዳት። እዛው በዛው ቋንቋቸው ሲደባለቅባቸው እንዴት መረዳትና የኃጢአታቸው ውጤት መኾኑን መገንዘብ አቃታቸው! እግዚአብሔር አምላካችን እንዳንስማማ የሚያደርገውን የሰናዖር ግንብ አፍርሶ በፍቅሩ ወደ እርሱ እንዲያቀርበን ኹሌም ሳንሰለች ልንለምነው ይገባናል። እግዚአብሔር አምላካችን በቸርነቱ ልቡናችንን ያብራልን።

ዮሐንስ ጌታቸው

09 Jan, 17:35


የገና አባት ስለ ተባለው ስለ ቅዱስ ኒቆላዎስ ያድምጡት።

ዮሐንስ ጌታቸው

07 Jan, 10:28


በዓለምም ከዓለም ውጭ ያለው ጌታ በቤተልሔም የታየበት ዕለት ነው፡፡ ይህ ሲባል አጥርተው ማየት በማይችሉ ዘንድ ውስን ብቻ የሚመስል÷ ነገር ግን በቅድስና መስታወት ለሚያዩት በአርያምም እየተመሰገነ በቤተልሔም የተወለደበት ዕለት ነው። ሰይጣን የደነገጠበትና ኃይሉ የደከመበት ዕለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በልደቱ ስፍራ መኾን አጋንንትን እንዳይቀርቡን ያደርጋል እልፍ አእላፋት መላእክት በዚያ ከበው ይጠብቁናልና። ተፈጥሮአዊውን ሕግ የገለበጠው ጌታ የተፈጥሮን ሕግ የሠራውና እንደፈቃዱም የሚያደርገው እርሱ መኾኑን ያወቅንበት ዕለት ነው። እንኳን በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ!

("ትምህርተ ጽድቅ" ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ)

ዮሐንስ ጌታቸው

07 Jan, 10:28


የጌታችን ልደት በአበው

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “የቅድስና ኹሉ ሰጭ ወደዚህ ዓለም የገባው በንጹሑ ልደት በኩል ነው። የቀደመው አዳም ከድንግል መሬት ተገኘ፤ ከእርሱም ያለ ሴት ዕርዳታ ሴት ተገኘች። ልክ አዳም ያለ ሴት ሴትን እንዳስገኘ፤ ድንግልም ያለ ወንድ በዚህ ዕለት ወንድን አስገኘች። ስለዚህ ሴቶች ለወንዶች ዕዳቸውን ከፈሉ፤ አዳም ብቻውን ሔዋንን እንዳስገኘ ድንግልም ያለ ወንድ ወንድን አስገኝታለችና። አዳም ያለ ሴት ሴትን ስላስገኘ ሊኩራራ አይገባም፤ ድንግልም ያለ ወንድ ወንድን አስገኝታለችና። በምሥጢሩ ተመሳሳይነት የተፈጥሮው ተመሳሳይነት ተረጋገጠ። ከአዳም ጎን አንዲት አጥንት ወሰደ ነገር ግን አዳም ጉድለት አልተገኘበትም÷ በተመሳሳይ ከድንግል ወንድ ልጅ ተወለደ ድንግልናዋ ግን አልተለወጠም” እያለ በሚያስደንቅ መንገድ የቅድስት ድንግል ማርያም ድንግልናን በአዳም ኅቱመ ጎን በኩል ያሳየናል”። ይህ የልደት ቀን የቅድስት ድንግል ማርያምን ክብር ከማሳየቱም አልፎ ሴቶችን እንዴት እንደካሰቻቸው ፍንትው አድርጎ ያመለክተናል። የጌታችን የልደት ዕለት ማለት የሴቶች ክብር የተገለጠበትና ወንድና ሴት እኩል መኾናቸው የተረጋገጠበት ዕለት ነው። “ሴቶች ሆይ የሴትነትን ክብር ያስመለሰችላችሁን ቅድስት ድንግል ማርያምን ትረሷት ይኾንን?”። ድንግል በድንግልና ወለደች ሲባል ሰምተን እንዳንደናገጥና ወደ ጥርጣሬ ባሕር ውስጥ እንዳንገባ አስቀድሞ አዳም ብቻውን ሔዋንን ሲያስገኝ ያለውን ነገር በመጽሐፍ አጻፈልን። አዳም ሔዋንን ብቻውን ከጎኑ እንዳስገኘ አምኖ የተቀበለ ሰው እንዴት ድንግል ማርያም በድንግልና ወለደች ሲባል ለማመን ይከብደው ይኾን? በጣም የሚያስገርመው ሔዋን ከአዳም ጎን ብትወጣም ለአዳም ውድቀትም ምክንያት ኾና ነበር፤ ድንግል የወለደችው ግን ዓለምን በሙሉ የሚያድን አምላክ ነው።

እንግዲህ በዚህ ዕለት የዓለም መድኃኒት ከድንግል ማኅፀን በቀለ!! ዓለም በሙሉ የተጠማውን የሕይወት ውኃ ለመጠጣት የተዘጋጀበት ዕለት ነው። ይህን ዕለት በመንፈሳዊ ደስታ ደስ ተሰኝተን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልናከብር ይገባናል እንጂ፤ በዘፈንና በስካር በቆሸሸ ሀሳብ በዓሉን አናበላሸው ። የልደቴ ቀን እያልን በቤታችን ኬኩን እና ሌላውን ሁሉ የምንበላ ኹሉ እውነተኛውን የልደት ቀን ማወቅ ከፈለጋችሁ ይህ ነው የልደታችሁ ዕለት/ቀን። በዚህ ቀን ጌታችን ስለሁላችን ድኅነት ብሎ ስለተወለደ የእርሱ የልደት ዕለት የእኛም የልደት ዕለት ነው። አዲስ አድሮጎ ሊወልደን በአምሳላችን ፈጣሪያችን የተወለደበት ዕለት የልደት ዕለታችን ኾኖ ካልተከበረ የቱ ቀን ሊከበር ነው። ዛሬ እውነተኛ ብርሃን ጨለማችንን ያርቅልን ዘንድ የወጣበት ዕለት ነው።

ዮሐንስ ዘክሮንስታድ “እኛን ከምድር አፈር የፈጠረንና የሕይወትን እስትንፍስ እፍ ያለብን ወደ ዓለም መጣ፤ በአንዲት ቃል ብቻ የሚታዩትንና የማይታዩትን ፍጥረታት ካለመኖር ወደመኖር ያመጣቸው እርሱ መጣ። ... የእርሱ መምጣት እንዴት ያለ ትሕትና ነው!! ምድራዊ ሀብት ከሌላት ድንግል በአንዲት ጎጆ ተወለደ፤ በድህነት ጨርቅ ተጠቅልሎም በበረት ተኛ።” እያለ የክርስቶስን በትሕትና መምጣት ያስረዳናል።

ይህቺ ዕለት ትሕትና በምድር ላይ የታየችበት የትሕትና ዕለት ናት። አዳም በትዕቢቱ ከቀደመ ክብሩ ቢዋረድም ክርስቶስ በትሕትና ከቀደመው ወደተሻለ ቦታ ከፍ አድርጎ አወጣው። በእርግጥ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነሥቶ ሰው ኾኖ የተገለጠበት አንዱ ምክንያት ለአርአያነት ስለኾነ÷ በትሕትና መታየቱ የሰው ልጅ ወደ መዳን ለመግባት የትሕትናንን ትምህርት ከራሱ ከባለቤቱ መማር ስላለበት ነው። በጌታችን የልደት ዕለት በትዕቢት የሚመላለሱ ልቦናዎች የጌታችንን የልደት ዕለት የረሱ ልቦናዎች ናቸው። እጅግ ዝቅ ማለት እጅግ ከፍ ያደርጋል፤ አምላክ ሰው ኾነ የሚለውን መስማት በምንም ቋንቋ ሊገለጥ የማይቻል እጅግ ጥልቅ የኾነ የትሕትና ውቅያኖስ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ነው የማይቆጠሩ ብዙ ጸጋዎችን ልናገኝ የቻልነው። እንግዲህ በዚህች ዕለት የትሕትናንን ትምህርት ቁጭ ብሎ መማርና የትሕትና መምህራችንን ማመስገን ያስፈልገናል። በዚህች ዕለት በተድላ ሥጋ ኾነው ስለ ትሕትና መምህር ስለክርስቶስ የመወለድ ምሥጢር ሳይማሩና በምሳሌ ሳይኾን በተግባር ወደ ጌታችን የልደት ዕለት ወደምትወስደን ቅድስት ቤተልሔም ለማድነቅና በምስጋና ከቅዱሳን መላእክት ጋር ለመደመር አለመሄድ እንዴት ያለ አለመታደል ነው!
ቃል ሥጋ የኾነው እኛን ከምድራዊ አኗኗር ወደ ሰማያዊ አኗኗር ለማሸጋገር ነው፡፡ ኀጥአንን ጻድቃን ለማድረግ፣ ከመበስበስ አንሥቶ ወዳለመበስበስ ሊያስነሣን፣ ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባርያ ከመኾን የእግዚአብሔር ልጅ ወደመኾን ሊያሻግረን፣ ከመዋቲነት ወደ ኢመዋቲነት፣ የእግዚአብሔር ልጆች ተብለን ከእርሱ ጋር የንጉሥ ልጆች አድርጎ ሊያከብረን መጣ፡፡ አቤት ገደብ የለሽ የእግዚአብሔር ርኅራኄ! አቤት የማይገለጽ የእግዚአብሔር ጥበብ! አቤት ታላቅ መደነቅ! የሰውን አእምሮ ብቻ የሚያስደንቅ ሳይኾን የቅዱሳን መላእክትን ጭምር ነው እንጂ!። የዛሬውን ዕለት ማክበር ማለት እነዚህን ኹሉ ጸጋዎች ለማግኘት መብቃት ማለት።

በዛሬው ዕለት ውስጥ ወደ መደነቅ ከፍ ያላለ ፍጥረት ማግኘት ፈጽሞ የማይቻል ነው። የእግዚአብሔር ጥበብ የጠላታችንን ጥበብ ያፈራረሰበት ዕለት ነው። የጌታችንን የልደት ዕለት በማያቋርጥ ምስጋና ልናክብር የሚገባን ከላይ የተዘረዘሩትን ልዩ ስጦታዎች ለመቀበል ነው። አንድ ሕፃን ልጅ በልደቱ ዕለት ስጦታ ቢሰጠው ገና እንደተወለደ ስጦታውን ስጦታ መኾኑን ተረድቶ ሊቀበል አይችልም፡፡ ዛሬ የምናከብረው የልደት ዕለት ግን ሕፃኑ ራሱ ልደቱን ለማክበር ለመጡት በቃላት የማይገለጽ ስጦታ የሰጠበት ዕለት ነው።

ቅዱስ አምብሮስ ደግሞ “ማርያም ከተፈጥሮ ሕግ በተቃራኒው በኾነ መንገድ ልጅ ወለደች የሚለው ለምንድን ነው አልታመን ያለው? ከተፈጥር ሕግ ውጭ ባሕር ዐየች ሸሸችም ዮርዳኖስም ወደ ኋላዋ ተመለሰች ተብሎ አይደለምን? መዝ 113÷3፣ ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ ከዓለት ውኃ ፈልቋል ዘጸ 17፣ ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ ውኃው እንደ ግድግዳ ቆሟል ዘጸ 14÷6፣ ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ ብረቱ በውኃ ላይ ተንሳፍፏል፣ ከተፈጥሮ ሕግ ውጭ ሰው በባሕር ላይ ተራምዷል” እያለ ይህ ታላቅ ሊቅ የእመቤታችንን ድንግልና ላለመቀበል ምንም ዓይነት ምክንያት መፍጠር እንደማንችል ይገልጥልና።

ስለዚህ በጌታችን የልደት ዕለት ከሰው ልጆች ልቦና የጥርጣሬ ድንጋይ ተነቅሎ ይወድቃል የተፈጥሮን ሕግ የሚቃረነው የድንግል በድንግልና መውለድ ይመሰከራል!! ዛሬ ሊብራሩ የማይችሉ ልዩ ኹነቶች የተፈጸሙበት ዕለት ነው፡፡ አምላክ የሰውን ሥጋና ነፍስ ተዋሕዶ ሰው ኾኖ የተገለጸበት፤ ድንግልም የማይወሰነውን አምላክ በማኅፀኗ ከመወሰንም አልፋ በታተመ ድንግልና የወለደችበት ዕለት ነው።

ድንግል ወለደች ተብሎ ከተፈጥሮ ሕግና ሥርዓት ውጭ በኾነ መንገድ የሚገለጽበት ልዩ ዕለት! የተፈጥሮ ባለቤትን በንጽሕት ሙሽራ በደንግል ማርያም ማኅፀን የራሱን ቤት በተዋሕዶ ሠርቶ የወጣበት ዕለት። ዛሬ ሰማይ ወለደች እንላለን፤ ግን ይህቺ ሰማይ ግሳንግሱ ፀሐይ የሚታይባት ሰማይ ሳትኾን የማይታየው ፀሐይ የሚታይባት ሰማይ ናት።

ዮሐንስ ጌታቸው

06 Jan, 05:29


https://youtu.be/yMMs1nqA1hc?si=oGDxA61KHIm_2HnO

ዮሐንስ ጌታቸው

05 Jan, 12:14


እባክዎትን መልካም ሥራ በደጅዎት አለችና "ሐመረ ብርሃንን" በጋራ እንተባበር፤ ይህን መልእክት ለብዙ ወንድም እኅቶች እንዲዳረስ እናድርግ🙏

ዮሐንስ ጌታቸው

05 Jan, 12:12


🗣 የበግ ቆዳ ያለው?

ለገና በዓል በቤትዎ ወይም በአካባቢዎ ከሚከናወኑ እርዶች የበግ እና የፍየል ቆዳን ለሐመረ ብርሃን በመስጠት የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ፣ ትውፊት እና ታሪክ ያስቀጥሉ።

የመቀበያ ቦታዎች ፦

📍ፒያሳ አሮጌው ፖስታ ቤት
📍ሰአሊተ ምሕረት
📍አየር ጤና ኪዳነ ምሕረት
📍መካኒሳ ቅዱስ ሚካኤል
📍ጀሞ መድኃኔዓለም
📍ገላን ልደታ ለማርያም

ለበለጠ መረጃ፦

📞09 66 76 76 76
📞09 44 24 00 00
📞09 09 44 44 55
📞09 44 17 61 26

ዮሐንስ ጌታቸው

02 Jan, 04:46


#ይህን_የነገረ_ክርስቶስ_ትምህርት_በዕርጋታ_ይመልከቱት፤ ለወዳጆቻችሁም አጋሩት።
https://youtu.be/GaEGn7lUjOs?si=_DPaLKXxMEoWnL7V

ዮሐንስ ጌታቸው

31 Dec, 18:15


#በተለይ_ወጣቶች_ብትሰሙትና_ለወዳጆቻችሁ_ብታጋሩት_ይጠቅማችኋል።

https://youtu.be/BLCs4GmEC4E?si=6PsKRIdPsQWPGl4o

ዮሐንስ ጌታቸው

25 Dec, 17:59


#እባክውትን_ከስሕተት_ትምህርት_ይጠበቁ_ዘንድ_ይሄን_ተከታታይ_የነገረ_ክርስቶስ_ትምህርት_ይስሙ። ለሌሎች ወንድም እኅቶችና ለተለያዩ ግሩፖች መላክን አይሰልቹ🙏

https://youtu.be/F63SwSg_x3o?si=PMDYdDBgu_88QaST

ዮሐንስ ጌታቸው

21 Dec, 17:38


#መዳን_በጸጋው_ብቻ_ነውን? ይመልከቱት። ለወዳጆቻችሁ አጋሩት።

https://youtu.be/Ax_PPB1jJjE?si=KO9JU96n5gVz6IlY

ዮሐንስ ጌታቸው

19 Dec, 14:50


ስለ ክርስቶስ ማንነት ተሳስተው ለሚያሳስቱ ሰዎች እጅግ ድንቅ ትምህርት!

👉አካል እና ባሕርይ

ተከታታይ የነገረ ክርስቶስ ትምህርት
                ክፍል 3

ነገረ ክርስቶስን ለመረዳት የሚጠቅመን ትምህርት በዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው

ሙሉ ቪዲዮውን ሊንኩን በመጫን ዩትዩብ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ ።
👇👇👇👇👇👇👇👇

https://youtu.be/Ty91w_Xc76w?si=_zrZ3JBkJ5LAg1-0

@MasyasTube

ዮሐንስ ጌታቸው

14 Dec, 16:42


https://youtu.be/yA_FNgX4J1M?si=9KxVFeJR_HCnJc_f

"በእምነት ብቻ መዳን" የሚለው ሐሳብ ሲፈተሽ!

ዮሐንስ ጌታቸው

11 Dec, 17:35


ተከታታይ የነገረ ክርስቶስ ትምህርት ስለ ኾነ፤ እባክዎት ለብዙዎች እንዲደርስ Share በማድረግ የበኩሎትን ይወጡ፤ በዚህ ቻናል ውስጥም ያላችሁ ተከታተሉት። ያልገባችሁ፣ እንዲብራራ የምትፈልጉት ካለ ንገሩኝ በቀጣይ የማነሣ ይኾናል።

ዮሐንስ ጌታቸው

11 Dec, 17:33


ቃል ሥጋ ሆነ ሲባል እንዴት ነው? የግድ ማወቅ ያለባችሁ ነገሮች!

ተከታታይ የነገረ ክርስቶስ ትምህርት
ክፍል 2

ነገረ ክርስቶስን ለመረዳት የሚጠቅመን ትምህርት በዲ/ን ዮሐንስ ጌታቸው

ሙሉ ቪዲዮውን ሊንኩን በመጫን ዩትዩብ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ ።
👇👇👇👇👇👇👇👇

https://youtu.be/ojCtAljvQR4?si=iOHzY7uP2_WEq3uH

@MasyasTube

ዮሐንስ ጌታቸው

07 Dec, 11:50


https://youtu.be/v3Wlrhnljfg?si=r3GnwZtJVBxMHzq7

ተከታታይ የነገረ ድኅነት ፖድካስት ነውና ተከታትላችሁ ብትመለከቱ ትጠቀማላችሁ።

ዮሐንስ ጌታቸው

04 Dec, 17:05


#በቦሌ_መድኃኔ_ዓለም_በአየር_መንገድ_ሠራተኞች_የተዘጋጀ_ሳምንታዊ_የማግሰኞ_መርሐ_ግብር_ተከታታይ_ትምህርት_በትንሹ_አዳራሽ_ከቀኑ_11፡50 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 1፡00 መጥተው መከታተል ይችላሉ።

https://youtu.be/LH-KCyHkWAA?si=6-EGxNXAG1g6c9gr

ዮሐንስ ጌታቸው

30 Nov, 09:33


እነዚህን ትምህርቶች እየገባችሁ ተከታተሉ፥ ለሌሎች ወንድም እኅቶችም አጋሩት።

ዮሐንስ ጌታቸው

30 Nov, 09:32


https://youtu.be/L4jqOOOxWUU?si=Kd4LDpOlqHv9-Jge

ዮሐንስ ጌታቸው

24 Nov, 06:35


https://youtu.be/fzL8OAF1TrU?si=v-0jgCKk30VX1RIe

ዮሐንስ ጌታቸው

19 Nov, 04:29


++++#ወጣትነትን_ምንድን_ነው?++++

ወጣት የሚለው ቃል በግእዙ ወሬዛ ተብሎ ይጠራል። ይኸውም "ወሬዛ" ጎልማሳ፥ ጎበዝ፤ ለጋ፣ ወጣት፥ ካሥራምስት ዓመት በላይ ያለ፤ ለዘር የበቃ፥ ለማልሞ፤ " እንዲል አለቃ ክፍለ ወልድ። (ኪዳነ ወልድ ክፍሌ (አለቃ)፣ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ፣ 2008 ዓ.ም፣ ገጽ 403)። ይህ ትርጒም ወጣትነት ምን እንደ ኾነ ዘርዘር አድርጎ ያስረዳል። ጎልማሳ የኾነ ማለትም በአንድ በኩል እንድገቱን ለማስረዳት የሚያግዝ ሲኾን በሌላ በኩል ከሕፃናት የተለየ ብስለትና አስተውሎት ያለው መኾኑን ይገልጻል። ዳዊት በጎልማሳነት ጊዜ መንገድን ቀና ማድረግ የሚቻለው እንዴት እንደ ኾነ ሲያስረዳ "በምንት ያረትዕ ወሬዛ ፍኖቶ። ወሬዛ (ጎልማሳ ወይም ወጣት) ግብሩን ጎዳናውን በምን ያቀናል ብትል፡ 'በዐቂበ ነቢብከ' (ቃልህን በመጠበቅ) ወይም ሕግህን በመጠበቅ ነዋ። አንድም እንዲህ ቢሉ ሕግህን በመጠበቅ አይደለምን? " ይላል። (ትንሣኤ ማተሚያ፣ መዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ፣ 2005 ዓ.ም፣ ገጽ 572)። ስለዚህ ርቱዕና ጣዕም ያለው ወጣትነት የሚበቅለው በቃለ እግዚአብሔር የተጠበቀ ሕይወት ሲኖር ነው። በግል ስሜትና ፍላጎት የምንጓዝና ለእግዚአብሔር ቃል ቦታ የማንሰጥ ከኾነ መጠበቅ አንችልም። ወደ ብዙ የኀጢአት ሐሳቦች እየበረርን የመግባት ዕድላችንን እያጠፋን ነው የምንሄደው። ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ "ከክፉ የጎልማሳነት (የወጣትነት) ምኞት ግን ሽሽ" በማለት ጢሞቴዎስን ያስጠነቀቀው። 2ጢሞ 2፥22። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ይሄን ሲያብራራ "የዘመናዊነት ምኞት ብቻ አይደለም ማንኛውም ተገቢ ያልኾነ ምኞት የወጣትነት ምኞት ነው። የበሰሉ ሰዎች የወጣቶችን ምግባራት እንዳያደርጉ ይማሩ። አንድ ሰው ለስድነት ወይም ለብልግና የተሰጠ ቢኾን ወይም ሥልጣንን አፍቃሪ ቢኾን ወይም ሀብትን አልያም ሥጋዊ ደስታን የሚያፈቅር ቢኾን ይህ የወጣትነት ምኞት ነው። እናም ይህ ደግሞ ጅልነት ነው።" ይላል። (ኀይለ ኢየሱስ መርሻ (ተርጓሚ)፣ 2ጢሞቴዎስ በቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ 2009 ዓ.ም፣ ገጽ 100-1)። ስለዚህ የወጣትነት ፈተናው ከባድ መኾኑን ልብ ማለት ተገቢ ነው።

መጋቤ ሐዲስ ስቡሕ አዳምጤ "ጎልማሳነት ወይም ወጣትነት ብዙ ፈተናዎች የሚያንዣብቡበት የሕይወት ጊዜ ነው። የወጣትነት ጊዜ ለመስማትም ለማየትም ለማድረግም ፈጣን የምንኾንበት ጊዜ ነው። ወጣትነት ሰዎች የሚያደርጉትን ሁሉ ለማድረግ ይገፋፋል። ጢሞቴዎስን በዚህ ወጥመድ ውስጥ እንዳይገባ ያስጠነቅቀዋል።" ይላሉ። (ስቡሕ አዳምጤ (መጋቤ ሐዲስ)፣ ከኤፌሶን እስከ ዕብራውያን ትርጓሜ፣ 2013 ዓ.ም፣ ገጽ 222)። እንግዲህ ወጣትነት ምን ያህል አስጨናቂ ጊዜ መኾኑን የምንረዳው ቅዱስ ጢሞቴዎስን ስንኳን ቅዱስ ጳውሎስ አስጠንቅቆ መምከሩን ስናስተውል ነው። በወጣትነት ጊዜ ወስጥ ለማንኛውም ድርጊታችን እጅግ በጣም ጥንቃቄ ማድረግ አለብን። ነገሮችን ቀለል አድርገን ከገባን በኋላ ስሕተት መኾኑን እንኳን ዐውቀን ለመውጣት ያስቸግረናልና። እንዲያውም ሊቁ ቅዱስ አምብሮስ "ወጣት ካህናት ባሏ ወደ ሞተባትና ድንግል ወደ ኾነች መሄድን ለተወሰነ ጉብኝት ካልኾነ በቀር መሄድን አይፈልግ። ይልቅ እንዲህ ላለው አገልግሎት ከፍ ያለ ካህን ወይም ጳጳስ ይሂድ። ዓለም እኛን እንዲተች እድል ለምን እንሰጠዋለን?" ይላል። (S.t Ambrose, On Duties of Clergy, 1፡20 (68, 87)። እንግዲህ በወጣትነት ውስጥ ያሉ አገልጋዮችም ቢኾኑ እኛ እኮ አገልጋይ ነኝ በማለት ራሳቸውን ማታለል የለባቸውም። አገልጋዮች አገልጋይ በመኾናቸው ምክንያት ራሳቸውን እያዘማነኑ መኖር ሳይኾን ያለባቸው የበለጠ ራሳቸውን እየጠበቁ ነው መኖር ያለባቸው። ቅዱስ ሄሬኔዎስ "ለደናግል ሴቶች ያለምንም ልዩነት ወይ እኩል ትኩረት ወይም እኩል ቸልታን ስጧቸው። ከእነርሱም ጋር በአንድ ጣራ (ቤት) ውስጥ አትቆዩ ወይም በቀደመው የንጽሕናችሁ ታሪክ አትመኩ። ከዳዊት በላይ ቅዱስ ከሰሎሞንም በላይ ጠቢብ አይደላችሁምና።" ይላል። (S.t Irenaeus, The author፡ pastoral love, p. 667 (in arabic) )።

ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የወጣትነትን ክብደት ለመግለጥ እንዲህ ይላል፦ "የወጣትነት ዕድሜ የአውሬነት ጊዜ ነው። በመኾኑም ብዙ ተቆጣጣሪዎች፣ መምህራን ርእሳነ መምህራን፣ አገልጋዮችና የግል መምህራን ያስፈልጉታል። እነዚህ ሁሉ ተደርገውለት የአውሬነቱ ጠባይ ከቆመ ደስታ ነው። ያልተገራ ፈረስ ወይም ለማዳ ያልኾነ የዱር አውሬ ማለት ነው ወጣትነት። ነገር ግን ከመጀመሪያው ጀምሮ ከልጅነት እድሜው አንሥቶ ከመልካም ሕግጋት ጋር እንዲጣበቅ ካደረግነው ብዙ ድካም ላይጠይቀን ይችላል። መልካም የኾኑት ልማዶቻቸው እንደ ሕግ ይቆጥራቸውና ጥሩነት የሕይወታቸው መመሪያ ና ሕግ ይኾናል።" በማለት ገልጾልናል። (ኀይለ ኢየሱስ መርሻ (ተርጓሚ)፣ የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ጢሞቴዎስ አንደኛይቱ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዳስተማረው፣ 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 105)። ወጣትነት በራሱ በባሕርዩ ክፉ አይደለም ነገር ግን ክፉ ምኞቶች፣ ዘማዊነት፣ ዘፋኝነት፣ ትዕቢተኝነት፣ ሰካራምነት፣ ሱሰኝነተ የመሳሰሉ ክፉ ሥራዎችን እንድናደርጋቸው ውስጣችንን ዲያብሎስ በእጅጉ የሚፈትንበት ወቅት ነወ።

ስለዚህ ወጣቶች በዲያብሎስ ፈተና ከተሸነፉ ሰነፎች ናቸው ካሸነፉት ደግሞ ጎበዝ መባላቸው ይታወቃል ማለት ነው። ወጣትነትን አውሬ የሚያሰኘው ልክ እንደ አውሬ የሚያስፈሩ አስተሳሰቦች የሚመነጩበት አንድም ወጣቶች አውሬአዊ ሥራ ለመሥራት የሚወዱበት ወቅት ስለ ኾነ ነው። በተፈጥሮ አይደለም በራሳቸው ፈቃድና ፍላጎት ነው እንጂ። በዓይን አይታየንም እንጂ በዝሙት ሱስ በሌላም ከባድ ኃጢአት ውስጥ ያለ ወጣት የሚመስለው ዲያብሎስን ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ግን ክርስቶስን እንድንመስለው ነበር የሚነግረን። በወጣትነት ጊዜ ከሚመጡብን ክፉ ፍላጎቶች ኹሌም ቢኾን ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

10 Nov, 11:45


#ከትዕይንተ_ግብረ_ዝሙት_ለመውጣት_ምን_እናድርግ፦

1) ኃጢአትን ለንስሐ አባት በግልጽ መናዘዝ። ፈርተን ገና ለገና ምን እባላለሁኝ በሚል ከደበቅነው፡ ከትዕይንተ ግብረ ዝሙት ሳንላቀቅ ነው የምንቀረው። ስለዚህ ለንስሐ አባት እያንዳንዷን ነገር ዘርዝሮ ለንስሐ አባት መንገርና በምክረ ካህን መኖር በእጅጉ ጠቃሚ ነው። ከዚህ ርኲስ የኾነ ግብር እንድንወጣ ኀይል ይሰጠናል፥ ከእኛ በተጨማሪ የንስሐ አባታችን አባታዊ ጸሎት ይረዳናል።

2) እግዚአብሔር እንዲያነጻህ፣ እንዲያድስህ፣ አእምሮህን እንዲለውጥልህ በጸሎት መጠየቅ። በተለይ ልበ አምላክ ዳዊት ኃጢአቱን አምኖ በተማኅልሎ ኾኖ የዘመራትን መዝሙር 50 በእርሱ ቦታ ራሳችንን አስገብተን ጸሎትን በዝማሬ ለእግዚአብሔር እናቅርብ። "አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ፤ እንደ ምሕረትህም ብዛት ኀጢአቴን ደምስስ። ከበደሌም ፈጽሞ እጠበኝ፥ ከኀጢአቴም አንጻኝ፤ እኔ በደሌን አውቃለሁና፥ ኃጢአቴም ሁል ጊዜ በፊቴ ነውና። አንተን ብቻ በደልሁ፥ በፊትህም ክፋትን አደረግሁ። ... በሂሶጵ እርጨኝ እነጻማለሁ፤ እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እኾናለሁ። ..." እያለ ልበ አምላክ ዳዊት ይዘምራል። መዝ 50፥1-7።

3) እግዚአብሔር አእምሮህን እውነት፣ የከበረ፣ ፍትሐዊ፣ ንጹሕ፣ የሚወደድ፣ ትእዛዛዊ በኾኑ ነገሮች እንዲሞላልህ በጸሎት መጠየቅ። ሰውነትን የሚቀድሱ ነገሮችን ለማድረግ በተግባር እየጣርን እግዚአብሔርን ደግሞ በጸሎት የምንጠይቀው ከኾነ ሕይወታችን እየቀናና እየተስተካከል ይሄዳል። ሰውነታችን የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ እንዲኾን "ሁለ ገብ የኾኑ የመንፈሳዊነት መገለጫዎችን በየቀኑ መለማመድ ወይም የሕይወታችን አካል ማድረግ፣ ለምሳሌ፦ የሥራ ፍቅር፣ ጥንቃቄ፣ ተስፋ፣ እምነት፣ ሐቀኝነት፣ ታማኝነት፣ ትሕትና፣ መነቃቃት፣ ወጥነት፣ ዓላማ ያለው፣ ፈጥኖ የመረዳት አቅም፣ የአመለካከት ከፍታ፣ አንድነት፣ ግልጽነት፣ ይቅር ባይነት፣ መረጋጋት፣ አገልጋይነት፣ ጥንካሬ፣ ሰላም፣ ታጋሽነት፣ አመስጋኝነት፣ ብስለት፣ ራእይ።" እነዚህን በደንብ እየተጉ ገንዘብ አድርጎ ለመንር መጋደል። (ስማቸው ንጋቱ (መጋቤ ምሥጢር)፣ የለውጥ አመራር ለቤተ ክርስቲያን፣ 2013 ዓ.ም፣ ገጽ 63)።

4) ሰውነታችን ቅድስናን ገንዘብ እንዲያደርግ መማር። ከልቡናችን ጥልቅ ሰውነታችን ቅድስናን ገንዘብ እንዲያደርግ መጣር። የሕይወት ዓላማ በቅድስና ከእግዚአብሔር ጋር መገናኘት መኾኑን ተረድተን በዚያ ውስጥ ለመኖር መጣር ያስፈልጋል።

5) የሩካቤ ሥጋን ትክክለኛ ትርጉሙን መረዳትና በተቀደሰ ጋብቻ ውስጥ ኾኖ ከባለቤት ጋር ብቻ ይህን በአግባቡ መፈጸም። የዝሙት ስሜት ሲያስቸግረንና ወደ ትዕይንተ ግብረ ዝሙት እየገፋፋ ሲያስቸግረን ወደ ቅዱስ ጋብቻ በቤተ ክርስቲያናዊ ሥርዓት ለመግባት ፈቃደ እግዚአብሔር በጾምና በጸሎት መጠየቅ። ምክንያቱም ፍትወት በእጅጉ አደገኛ እሳት ነው። ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ "ፍትወት እሳት ነው፤ ያውም የማይጠፋና ዘወትር የሚኖር እሳት፤ ፍትወት ማለት እንደ ተበከለና ዕብድ ውሻ ነው። ምንም ያህል ከእርሱ እንሽሽ ብትሉም ኹል ጊዜ ወደ እናንተ ፈጥኖ ይመጣል፤ ይህን ማድረጉንም መቼም መች አያቆርጥም። የእቶን እሳት ክፉ ነው፤ የፍትወት እሳት ግን ከእቶን እሳት ይልቅ አረመኔ ነው። በዚህ ጦርነት ውስጥ የተኩስ ማቆም ስምምነት የሚታሰብ አይደለም። በሕይወተ ሥጋ እስካለን ድረስ ከዚያ ውጊያ ውጪ ኾኖ መኖር የሚገመት አይደለም። ዘወትር ውጊያ አለ። ይህ የሚኾነውም ሽልማቱም ታላቅ ይኾን ዘንድ ነው። ብፁዕ ጳውሎስ ኹል ጊዜ የሚያስታጥቀንም ለዚሁ ነው፤ ውጊያው ኹል ጊዜ ስለ ኾነ ጠላት ኹል ጊዜ ንቁ ስለ ኾነ።

ፍትወት ከእሳት ባልተናነሰ መልኩ እንደሚያቃጥል መማር ትወዳላችሁን? ሰሎሞንን አድምጡት፤ እንዲህ ያለውን "በፍም የሚሔድ እግሮቹ የማይቃጠሉ ማን ነው? ወደ ሰው ሚስት የሚገባም እንዲሁ ነው፤ የሚነካትም ኹሉ ሳይቃጠል አይቀርም" ምሳ 6፡28-29። እንግዲህ የፍትወት እሳት ከተፈጥሮ እሳት ጋር እንዴት እንደሚነጻጸር ታያላችሁን? እሳትን የሚነካ ሰው ሳይቃጠል መመለስ አይቻለውም። የቆነጃጅትን ፊት ዐይቶ የሚመኝ ሰውም ከዚያ እሳት በላይ ነፍሱን ያቃጥላል። አንድን ሰው በዝሙት ዐይን መመልከት ለሰውነት እንደ ላምባ ነው። ስለዚህ ምክንያት እኛም የዚህ ዓለም ነገሮችን በዚሁ መልኩ ልንመለከታቸው አይገባም፤ የፍትወት ነዳጆች ናቸውና።" በማለት ይገልጻል። (ገብረ እግዚአብሔር ኪደ (ተርጓሚ)፣ ወደ ቴዎድሮስ፡ ታኅሣሥ 2009 ዓም ገጽ 8-9)። እንግዲህ የጋብቻ አንዱ ጥቅም ሰይጣን በሰውነታችን የሚያነደውን የፍትወት እሳት ለማብረድ መኾኑን ልብ ይሏል።

6) በመንፈስ ቅዱስ ምሪት መሠረት መጓዝ። በመንፈስ ቅዱስ ሐሳብ የምትመራ ከኾነ ወደዚህ ሐሳብ አትገባም። በእኛ ውስጥ ስሜት (Emotion)፣ ዕውቀት (Knowledge) እና መንፈሰ እግዚአብሔር (Holy Spirit) አለ። በዚህ መሠረት በስሜታችን ብቻ የምንመራ ከኾን ስሜታዊ ስለምንኾን ትዕይንተ ግብረ ዝሙትን የማየትን ዕድላችንን እናሰፋለን ማለት ነው። በዕውቀታችንም ሲኾን፡ ነገሮችን በእኛ አእምሮ ልክ የምንመጥንና የምንመዝን ከመኾንም አልፈን እኛ ልክ አይደለም ብለን ካሰብን ማንንም የማንሰማ እንኾናለን። እነዚህ ኹለቱ መንገዶች ጎጂዎች ናቸው። ስለዚህም በመንፈሰ እግዚአብሔር የምንመራና ስሜታችንንና ዕውቀታችንን ቅዱስ በኾነው በእግዚአብሔር መንፈስ ቁጥጥር ስር አድርገን የምንጓዝ ከኾነ፡ ትዕይንተ ግብረ ዝሙት ይቆጣጠረን ዘንድ አይቻለውም።

7) ወደ ትዕንተ ግብረ ዝሙት የሚወስዱህን ነገሮች በሙሉ ለመግታት መጣር። ፊልሙን፣ ማኅበራዊ ሚዲያውን ተወት ማድረግ ያስፈልጋል። ማኅበራዊ ሚዲያዎች በዋነኛነት ወደ ትዕይንተ ዝሙት እንድንሳብ ቅስቀሳ ስለሚያደርጉብን ከዚህ ስሜት እስክንወጣና በመንፈሳዊነት እስክናድግ ከሚዲያ ራሳችንን ራቅ ብናደርግና፥ ኃይል አግኝተን መንፈሳዊ ነገሮችን ብቻ እየመረጥን ለመጠቀም መትጋት አለብን።

8) ከትዕይንተ ግብረ ዝሙት የሚያስወጡ እርምጃዎችን ለመውሰድ አትዘገይ። ምክንያቱም 1000 Km ርቀት ያለውን መንገድ ከ1Km ተጀምሮ እንደሚደረስበት ቸል ማለት አይገባምና። ብዙ ጊዜ እየጎዳን ያለው ቁርጥ ውሳኔ አለመወሰናችን ነው። ውሳኔያችን ከጥልቅ የልቡናችን መሠረት ከኾነ፡ የማሸነፍ ኀይላችን ይጨምራል። ወስነን ማስወገድ ከጀመርን በኋላ ወደ ኋላ መመለስ የለብንም፡ ወደ ፊት እየገሠገሡ መሄድ እንጂ!

9) በትዕይንተ ግብረ ዝሙት የሚመጣውን አደጋ ለመፍታት ከመጣር ይልቅ ወደ ትዕይንተ ግብረ ዝሙት የሚወስደውን ምክንያት መፍታት ወይም ማጥፋት ላይ ማትኮር። ይህ አካሄድ ሥሩን ነቅለን እንድንጥለው ያደርጋል። ወደ ትዕይንተ ዝሙት የሚመራንን መሠረት ለመናድ በእጅጉ ይጠቅመናል። ስለዚህም ዋናውን መሠረት እስካላገኘን ድረስ እንደ ፓራስታሞል መፍትሔ ብለን የምናቀርባቸው ነገሮች ሁሉ ከተወሰነ ማስታገስ በቀር በሽታው ተመልሶ እንዳይነሣ ከማድረቅ በቀር ጥቅም የሌላቸው ሊኾኑብን ይችላሉ። ስለዚህም መሠረቱን ነቅሎ ለመጣል ወደ ትዕይንተ ግብረ ዝሙት የሚወስዱንን ነገሮች በሙሉ ነቅሶ ዘርዝሮ እነርሱን መከላከልና ማስወገድ ላይ መሥራት በእጅጉ ጠቃሚ ነው።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

06 Nov, 05:43


#እንደ_ግል_አዳኝህ_አድርገህ_ተቀበለው_ይባላልን?

መናፍቃን ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኝህ አድርገህ ተቀበል ማለታቸው ትክክል ነውን? በፍጹም ትክክል አይደለም፡፡ ሲጀመር ይህ ዓይነቱ እምነት የሚመነጨው ትምህርቶችን በሙሉ “ብቻ” በምትል ቃል ውስጥ ከመክተት ነው። እምነት ብቻ፣ ጸጋ ብቻ፣ መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ፣ ኢየሱስ ብቻ የመሳሰሉትን ትምህርት በልቡ የጸነሰና በአፉ የወለደ ኹሉ ዞሮ ክርስቶስን በብቻ መርሕ ውስጥ ከትቶ እንደ ግል አዳኝ አድርገህ ተቀበለው ቢል ብርቅና ድንቅ አይደለም። ደግሞ አለማስተዋል ካልኾነና ቅዱሳት መጻሕፍትን ለመረዳት አለመፈለግ ካልታከለበት በቀር ማዳንን ለኢየሱስ ክርስቶስ ብቻ መስጠት ትክክል አይደለም፡፡ ማዳን የአብ የወለድና የመንፈስ ቅዱስ የአንድነት ውጤት ነውና፡፡ ቤዛነት ወይም መሥዋዕትነት ወይም የሰው ልጆችን ተክቶ (በተገብቶ) የተፈጸመው ሥራ ወልድ በሥጋዌው በተለየ አካሉ ያደረገው ነው፡፡ ይህንን ለአብና ለመንፈስ ቅዱስ ሰጥተን አንናገርም፡፡ ምክንያቱም በተለየ አካሉ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ በአዳም ቦታ ተገብቶ ራሱን ቤዛ አድርጎ ያቀረበው አማናዊው መሥዋዕት እርሱ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና። ይህን በተመለከተ ሩሲያዊው ቭላድሚር ሎስኪ የተናገረውን መ/ር ፀሐዬ ደዲማስ እንዲህ ተርጒሞልናል፡- "በእርግጠኝነት (የድኅነት) ሥራ የሚከናወነው ልዩ በኾነው ማንም በማይጋራው በሥላሴ ፈቃድ ነው፤ በእርግጠኝነትም የዓለም (የሰው ልጆች) ድኅነት የዚህ አንድና የጋራ የኾነው የሦስቱ አካላት ፈቃድ ውጤት ነው፡፡ … ነገር ግን ይህ አንድ ፈቃድ በድኅነት ሥራ ላይ የተፈጸመው በእያንዳንዱ አካል በተለያየ ኹኔታና አፈጻጸም ነው፤ አብ ላከ ወልድ ታዘዘ (ተላከ) መንፈስ ቅዱስ ደግሞ ያከናውንና ይረዳ ነበር፤ በዚህም ወልድ ወደ ዓለም ገባ፡፡ የወልድ ፈቃድ ያው ራሱ የሥላሴ ፈቃድ ነው፤ ነገር ግን የተገለጠው በመታዘዝ ወይም በመላክ ነው፡፡ እኛን ያዳነን ሥላሴ ነው፤ ነገር ግን የድኅነትን ሥራ እውን ለማድረግ ሰው ኾኖ (በተለየ አካሉ) የተገተጠው ወልድ ነው፡፡" ይላል፡፡ ስለዚህ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን መናፍቃንን ይህን ጉዳይ ልብ እንዲሉ ትመክራለች፡፡

በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ክርስቶስ ዓለምን ያዳነው እያንዳንዱን ግለ ሰብእ እየዞረ በማዳን አይደለም፡፡ ማለትም 1000 ሰዎች ቢኖሩ ለሁሉም በየግል እየሄደ እየተሰቀለ ድኅነትን አልሰጠም፡፡ አንድ ጊዜ በመስቀል ላይ ለዓለም ሁሉ ተሰቅሎ፡ ራሱን ቤዛ አድርጎ ዓለምን አዳነ እንጂ፡፡ የተጸነሰውም፣ የተወለደውም፣ የተገረፈውም፣ የተሰቀለውም፣ ወደ መቃብር የገባውም፣ ሞትን ድል አድርጎ የተነሣውም፣ ያረገውም ለግለ ሰብእ ሳይኾን አንድ ጊዜ ለዓለም ሁሉ ነው፡፡ ዓለምን ሁሉ አንድ ጊዜ ስላዳነ የዓለም ሁሉ መድኃኒት ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ የዓለም ሁሉ አዳኝ መኾኑን ስንናገር ዓለም በተባለው ውስጥ የሰው ልጆች ሁሉ መኖራቸው ግልጽ ነው፡፡ ስለዚህ የሰውን ልጆች በሙሉ ሲያድን እንዳንዱን ግለ ሰብእ ማዳኑን ልብ ይሏል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስን የዓለም አዳን ስንል የሰውን ልጅ በሙል ከጽንስ እስከ ዕርገት በፈጸመው ቤዛነት በአንዴ ማዳኑን ለመግለጽ ነውና፡፡ ሁሉን በማዳን ውስጥ እያንዳንዱን አድኗል እንጂ እያንዳንዱን እያዳነ በመጨረሻም ሁሉን ወደ ማዳን የደረሰ አይደለም፡፡ እንግዲህ ሁላችንንም በየግላችን ሳይኾን በአንድነት ያዳነንን እንዴት በየግል ብቻ እንዳዳነን አደርገን የግል አዳኝ እንለዋለን?

በእኛ ቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት እያንዳንዱ አማኝ ክርስቶስን መድኃኒቴ ማለት ቢችልም የግሌ መድኃኒት ግን አይልም፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ስትጸልይ "… ነፍሴ በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴትን ታደርጋለች …" በማለት አርአያ ኾናናለችና፡፡ ስለዚህ መድኃኒቴ፣ አምላኬ እንለዋለን ነገር ግን የግሌ መድኃኒት፣ የግሌ አምላክ አንለውም፡፡ ምክንያቱም የግሌ የሚለው አገላለጽ የሌሎችስ አይደለም እንዴ የሚል ጥያቄን ይፈጥራልና፡፡

በሌላ በኩል ካየነው ድኅነት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውጭ የሚቻል እንደ ኾነ ያስመስላል፡፡ ምክንያቱም ከቅድስት ቤተ ክርስቲን ውጭ ኾኜ በግሌ ክርስቶስ ያድነኛል ማለት ፈጽሞ ስሕተት ነውና፡፡ ድኅነት ከቤተ ክርስቲያን ውጭ ፈጽሞ የማይኾን ነውና፡፡ የመዳን መንገዶች በሙሉ ተዘርግተው የተቀመጡት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ነውና፡፡ አንድ ሰው ሌላው ቀርቶ ቤተ ክርስቲያን አታስፈልገኝም ብሎ በግሉ ጾም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ ምጽዋዕት እና የመሳሱት አድርጎ እዳናለሁ ካለ እንኳን በፍጹም ተሳስቷል፡፡ ምክንያቱም በግል ብቻ ኾኖ መዳን አይቻልምና፡፡ ለመዳን የግድ ማመን፣ መጠመቅ፣ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል፣ ኃጢአት ሲሠራ ንስሐ እየገባ እንደ ገና ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል፣ መልካም ሥራዎችንም መሥራት አለበት፡፡ በዚህ መሠረት ለመጠመቅ፣ ለመቁረብ እና ንስሐ ለመግባት የግድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መኖር አለበት፡፡ እነዚህን ነገሮች በግሉ ብቻ ሊያደርጋቸው አይችልምና፡፡ ሌላው ቀርቶ በምንሠራው መልካም ሥራ እንኳን ብዙ ጉድለቶች ስለሚኖሩብን በቅዱሳን ቅድስና አምነን በስማቸው ቀዝቃዛ ጽዋ ውኃ የተጠሙትን ማጠጣት አለብን፡፡ ይህን ሁሉ መስመር የዘረጋው አምላካችን ክርስቶስ ነውና፡፡ እምነታችንም ቢኾን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን መሠረት ላይ ካለው ውጭ ከኾነ መዳን አይቻልም፡፡ ስለዚህ በምንም መንገድ ብናስብ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውጭ ኾነን በግል መዳን አንችልም፡፡ እንግዲህ "እንደ ግል አዳኝ አድርገህ ተቀበል" ማለት ከላይ ከተዘረዘሩት መሠረታዊ የመዳን መንገዶች ውጭ እድናለሁ ብሎ ማሰብ ነውና ፍጹም ስሕተት ነው፡፡ ያለ ቤተ ክርስቲያን እምነት፣ ያለ ቤተ ክርስቲያን ጥምቀት፣ ያለ ቤተ ክርስቲያን ቁርባን እና ምሥጢረ ንስሐ መዳን ፈጽሞ የማይታሰብ ነገር ነውና፡፡

ከላይ የገለጽነውን ጉዳይ አጽንዖት ሰጥቶ ታላቁ ሊቅ ቆጵርያኖስ "ማንም ቢኾን ራሱን ከቤተክርስቲያን ለይቶ ከአመንዝራዎች ጋር ቢቀላቀል፤ ከቤተክርስቲያን ቃል ኪዳን ይለያል፤ ቤተክርስቲያንን ትቷት የሄደ የክርስቶስን የክብር አክሊል አያገኝም። እርሱ እንግዳ ነው፤ እርሱ የተቀደሱ ነገሮችን የሚያቃልል ነው፤ እርሱ ጠላት ነው። ቤተክርስቲያን እናቱ ያልኾነችለት እግዚአብሔር አባቱ አይኾንለትም። ማንም ከኖኅ መርከብ አምልጦ ውጭ ከኾነ ከቤተክርስቲያንም ውጭ ይኾናል በማለት የኖኅ መርከብ የተባለችውን ቅድስት ቤተክርስቲያንን ትቶ መሄድ ተገቢ አለመኾኑን ያስረዳል። በመኾኑም ድኅነት የሚገኘው የጸጋው ግምጃ ቤት በኾነች በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በኩል መኾኑን ልብ እንበል፡፡ ስለዚህ እንደ ግል አዳኝህ አድርገህ ተቀበል የሚለውን ከላይ ያብራራነውን መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት የሚንድ ክሕደታዊ ሐሳብ መኾን እንስተውል፡፡ ... !

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

03 Nov, 16:02


+++++#ነጻነታችንን_አናስወስደው+++++++

እግዚአብሔር በፍጥረት ጊዜ ለሁላችንም ከሰጠን መሠረታዊ ነገሮች ውስጥ አንዱ ነጻ ነት ነው። በዚህ ስጦታ አማካኝነት ሰጪውን እግዚአብሔርን ምን ያህል ቸር እንደ ኾነ እናጣጥምበታለን። በተለይ በሐዲስ ኪዳን ያገኘነውን ነጻነት በተመለከተ ዮስጢኖስ እንዲህ ይላል “በእውነታው አንድ ነጻነት ብቻ ነው ያለው። ይኸውም ከኃጢአት፣ ከክፋትና ከዲያብሎስ ነጻ ያደረገን የክርስቶስ ቅዱስ ነጻነት ነው። በዚህ ከእግዚአብሔር ጋር እንገናኛለን። ሌሎች ነጻነቶች በሙሉ እውነት የሚመስሉ፣ የተሳሳቱ፣ በእርግጥም በአጠቃላይ ባርነቶች ናቸው" (St. Justin Popovich, Ascetical and
Theological Chapters, II.36) አንድ ሰው ከእግዚአብሔር ተለይቶ የወደደውን ለማድረግ በመፈለጉና አንዳንዴም ተሳክቶለት በማድረጉ ምክንያት የተሰጠውን ስጦታ ተጠቅሟል ማለት አይደለም። ነጻነታችንን መልካም የኾነውን ለመምረጥ ብቻ የማንጠቀም ከኾነ እንጎዳበታለን። እግዚአብሔር ነጻነትን የሰጠን ከልባችን እርሱን ፈልገን እንድናመልከው ስለሚፈልግ ነው። ክርስቲያን ማለት ክርስቶስን የሚመርጥና ፈቃዱን በማድረግ ደስ የሚሰኝ ማለት ነው። ከእውነተኛው ነጻነት እውነተኛ ደስታ ይመነጫል፤ ይህ ደስታ ደግሞ የእኛ ብቻ ሳይኾን የሰማይ መላእክትም ደስታ ነው።

ፍጹም የኾነውን ነጻነት የምናገኘው በፍቅረ እግዚአብሔርና በፍቅረ ቢጽ ውስጥ ነው። ፍቅር የሌለው ሰው ነጻነት የለውም። እግዚአብሔርንና ሰውን የምንወድ ከኾነ ፍጹሙን ነጻነት ገንዘብ አድርገናል ማለት ነው። በዚህ ውስጥ ደግሞ ፍጹም የኾነ እኩልነት አለ። ስሎዋን እንዲህ ይላል “ሁሉም ሰው ንጉሥ፣ አባት፣ አለቃ መኾን አይችልም። ነገር ግን በማንኛውም የሥልጣን ደረጃ ውስጥ ኾኖ እግዚአብሔርን መውደድና ማስደሰት ይችላል፤ ይህ ብቻ ጠቃሚ ነውና። ማንም እግዚአብሔርን በምድር ላይ አብልጦ ቢወድ፣ በእግዚአብሔር መንግሥት በታላቅ ክብር ይኾናል።" (St. Silouan the Athonite, Writings, VI.23)። እንግዲህ በእውነተኛው ነጻነት ውስጥ መኖር ማለት እግዚአብሔርን በማፍቀርና በማስደሰት መኖር ማለት ነው። በነጻነት ውስጥ አለን ማለት በዚህ መልካም ነገር ውስጥ አለን ማለት ነው።

ተወዳጆች ሆይ! ይህን ቅዱሱን ነጻነት ክፉ ምኞታችን አላጠፋብንምን? የዚህ ዓለም ኃላፊ ነገሮች እጅግ በጣም ደስ የሚያሰኙን ራሳችንን ለኃጢአት ባርያ በማድረጋችን ምክንያት ከቅዱሱ ነጻነች ስለ ራቅን መኾኑን መዘንጋት የለብንም። ሐሳባችን ከመልካምነት ሲወጣ አእምሯችን ለአጋንንት ባርያ ወደ መኾን መውረዱን እናስተውል! ቶሎ ብለንም ውስጣችንን እንመርምር፥ ስለ ፍቅር ብሎ ፈጥሮን በፍቅሩ የሚያኖረንን አምላክ የሰጠንን ነጻነት ፍሬ በማፍራት እናስደስተው! ለዚህ ዓለም ማንኛውም ኃላፊ ነገር ውስጣችንን ባርያ በማድረግ ነጻነታችንን አናበላሽ። እስከ ዛሬ ድረስ የፈጸምናቸው ክፉ ሥራዎች እጅግ መብዛታቸውን አስበን ፈጣሪያችንን በአንብዓ ንስሓ ማረን እንበለው።

ቅዱስ ማርቆስ “መንፈሳዊ ሕይወትን የሚኖር ትሑት ሰው፥ ቅዱሳት መጻሕፍትን በሚያነብበት ጊዜ፥ ሁሉንም ነገር ከራሱ ሕይወት ጋር ያገናኛል እንጂ ከሌሎች አይደለም።" ይላል። (St. Mark the Ascetic, Sermon, 1.6)። ስለዚህ ነጻነትን ጠብቆና ቀድሶ ለመኖርን የራስን ሕይወት መመርመር ያስፈልጋል። የራሳችንን ሕይወት ሳንቀድስ ስለ ሌላው ብቻ በማወራት የምንኖር ከኾነ በአጋንንት ወጥመድ ውስጥ መጠመዳችንን ልብ እንበል! ለዚህም ነው ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “ብርሃን የሌላቸው ቀጥ ብለው መሄድ እንደማይችሉ የቅዱሳት መጻሕፍትን ጨረር ያላዩ በጨለማ ስለሚጓዙ ኃጢአትን ይሠራሉ።" (St. John Chrysostom, Conversations on the Epistle to the Romans, 0.1)። በመኾኑም ነጻነታችንን በቅዱሳት መጻሕፍት መመሪያ ውስጥ እናድርገው። በራሳችን ምድራዊ ፍላጎት ምክንያት እግዚአብሔር የሰጠንን ልዩ ስጦታ በሰይጣን አናስወስደው! እግዚአብሔር በቸርነቱ ይጠብቀን፥ በብዙ የኃጢአት ዱላ ተደብድቦ የደነዘዘውን ልቡናችንን ይፈውስል፤ የሐሳቡንም ብርሃን በልባችን ያብራልን፤ በፈቃዳችን ከታሠርንበትን የኃጢአት ባሪነት በቸርነቱ ያላቅቀን፤ ቅዱስ ቃሉንም ወደ መረዳትና በገቢራዊ ሕይወት ወደ መኖር ልዕልና ያሣርገን አሜን።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

01 Nov, 18:35


https://youtu.be/cTrW_171w-M?si=sLzjkUY0_CiYz5Sj

ዮሐንስ ጌታቸው

29 Oct, 06:30


#ይህን_ማስታወቂያ_ለብዙ_ሰዎች_አድርሱ!

ሰርዲኖን መጽሐፍ ቤትን ይጎብኙ። የተለያዩ መጻሕፍትን በቅናሽ ያገኛሉ።

የርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳን አሐቲ ድንግል ጸያሔ ፍኖት፡ ወግሪስ እና ምዕዳንን ለምትፈልጉ በሙሉ በ 0910934578 እየደወላችሁ ማዘዝ ትችላላችሁ።

አድራሻ- ቅድስተ ማርያም በምሥራቅ በር ሸዋ ዳቦ ቤትን አልፈው ትንሽ ወረድ ሲሉ ከምስራች ማዕከል ዝቅ ብሎ ከሚገኘው የገቢያ ማዕከል እንገኛለን።

ለበለጠ መረጃ 0910934578

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

28 Oct, 07:13


+++በሚዲያ ላይ የሚታዩ ክፉ ልምምዶች!+++

ውድ ወንድም እኅቶቼ እንደ ምን ሰነበታችሁ? እግዚአብሔር ይመስገን እኔ ደኅና ነኝ። ዛሬ በጣም በአጭሩ በሚዲያ የምናገኘውን ጥቅም ትቼ ችግር እየኾኑ ያሉ ነገሮችን ለማንሣት ፈለግኹ። በቲክቶክ፣ በቴሌግራም ግሩፖች እና አንዳንዴ በፌስ ቡክ አንዳንድ ነገሮችን እያየኹኝ ለምን? አይጎዳምን? እያልኩ ለራሴ ጥያቄ የምጠይቅባቸው ጉዳዮች አሉኝ። ሌሎቻችሁም ቢኾን እንዲህ ባይኾን የተሻለ ነበር የምትሉባቸው የተለያዩ ነገሮች ሊኖሩ ይችላሉ። እኔ ግን የእኛ ልጆች የሚያነሷቸውን ክፉ ልምምዶች በአጭሩ ላንሣ፦

1) ቀኖናን ቀለል አድርጎ የማየት መሠረታዊ ችግር አንዱ ነው። ለመኾኑ ቀኖናን ቀለል አድርገን እንድናየው ማን ነው የፈቀደልን? ቀኖናንስ አልቀበልም ማለት ምንም ችግር እንደ ሌለው እንዴት እርግጠኛ መኾን ቻልን? ይህን ጥያቄ የማቀርበው በዘመኑ አነጋገር "ዘና ፈካ" ብለው ይሄ ቀኖና ስለ ኾነ አልቀበልም የሚሉ ወንድሞች እና እኅቶች በርከት እያሉ ይመስላል። ይህ እጅግ በጣም ክፉ ልምምድ ነው። በባሕር ላይ የሚሄድ መርከብ ትንሽዬ ቀዳዳ ካለው ዕድል ፈንታው በዚያች ቀዳዳ ከሚገባው ውኃ የተነሣ ወይ መሠበር ወይም መስመጥ ነው። በሕይወት ልምምድም ቢኾን ሰይጣን የሚጀምረው አባ ማርቆስ ባሕታዊ እንዳሉት ትንሿን ኃጢአት ከማላመድ ነው። የምዕራቡን ዓለም ክርስትና አፈር ከድሜ ያበላው ከቀኖና መውጣት መኾኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል። ስለዚህ ቀኖና ነው! ባልቀበል ችግር የለውም እያሉ ወደ ክፉ ልምምድ ከመሄድ ይልቅ ቀኖና ምንድን ነው? በጥቅሉ ቀኖናን አልቀበልም ማለት ተገቢ ነውን? ቀኖናንስ አለመቀበል ለምን ይዳርጋል? ለመኾኑ ስንት ዓይነት ቀኖና አለ? የሚስተካከል ቀኖና ካለ ማን ነው መናገር ያለበት? አንድ ምእመን ይህን ቀኖና አልቀበልም ይህን እቀበላለሁኝ እያለ ማወጅና በገሃድ ለሕዝብ መናገር ይችላልን? ይህን በአግባቡ ከመጻሕፍት አንብበው ሳይረዱ አልቀበልም እቀበላለሁኝ ማለት ክፉ ልምምድ ነው።

2) መሠረታዊ የሃይማኖት ጉዳዮች ላይ ያለ ጥንቃቄና ፈሪሓ እግዚአብሔር በመሰለኝና በራስ መረዳት ልክ ብያኔ ለመስጠት መዳዳት። ለምሳሌ እኔ በቀጥታ የሰማኹት ሥግው ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ አብን አምልኳል በሎ መናገር። ይህን በተመለከተ የአበውን አረዳድ በአጭሩም ቢኾን ከዚህ ቀደም አስነቤያችኋለሁ። በመጻሕፍት የተገኙ ምንባባትን ሳይጠነቀቁ በድፍረት መናገርን ችግር አድርጎ አለማሰብ። ሌላም ልጨምር ሥግው ቃል ስንት ፈቃድ አለው? ሲባል ከኹለት የተገኘ አንድ ፈቃድ። የትስብእት ፈቃድ የለምን? ሲባል ለዘላለም የትስብእት ፈቃድ ለመለኮት ፈቃድ ሲገዛ ይኖራል ብሎ መመለስ። እንዲህ ዓይነቱን አገላለጽ መልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ በመድሎተ አሚን መጽሐፍ "... ስንሰማው እንኳን ይቀፈናል" ይሉታል። የትስብእት ፈቃድ ለመለኮት ፈቃድ በሥግው ቃል ውስጥ የሚገዛ ከኾነ፤ በአንዱ ሥግው ቃል ውስጥ ተገዢና ገዥ የኾኑ ኹለት ፈቃዳት አሉ ማለት ነው። ይህ ካልኾነ ከተዋሕዶ በኋላ የሥግው ቃል ፈቃድ ከመለኮት ፈቃድ ተለይቶ የት ይገኝና ነው የሚገዛው? አኹን በዝርዝር አናነሣውም። ግን የድፍረትና ኹሉን እመልሳለሁኝ የማለት መንፈስ ያለበት አካሄድ ነው። ኹሉን የሚብራራና የሚታወቅ አድርጎ የማሰብ ዝንባሌ የምዕራባውያን የነገረ መለኮት አረዳድ መንገድ ነው። ክፉ ልምምድ ነው።

3) የኢትዮጵያን አባቶች ቀለል አድርጎ ማየት። ታድሮስ ያዕቆብ ማላቲንን እና አንዳንድ ግብጻውያንም ኾኑ የውጭ ሊቃውንትን፣ ከኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ከነ አድማሱ ጀንበሬ፣ አለቃ አያሌው ታምሩ፣ ሊቀ ጒባኤ አባ አበራ በቀለ፣ ከሊቀ ሊቃውንት እዝራ ሐዲስ፣ ከነ ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ... አስበልጦ ማሳሰብ። በአባቶች መካከል መበላለጥን ማላመድ። የእኛዎቹ የሚያስተምሩትን ማስጠርጠር ሲያስፈልግ ደግሞ በድፍረት ልክ አይደለም፥ እንዲህ የሚባል ነገር የለም እያሉ ራስን ደምዳሚ አድርጎ ማቅረብ። ከግእዙ ይልቅ የእንግሊዘኛውን ምንጭ የበለጠ ታማኝ አድርጎ ማሰብ እና መሰል ነገር ክፉ ልምምድ ነው።

4) በኢትዮጵያ ያሉ ገድላትን፣ ድርሳናትንና ተአምራትን ያለ ሞያዊ ጥናት እጅጉን መጠርጠር። ኹል ጊዜ ስሕተት አለባቸውን የሚለውን ብቻ አጽንኦት እየሰጡ ምእመናንን ለማሸሽ መጣር። ከዚህ በተጨማሪ አንድ ጽሑፍ ለራስ አእምሮ ትክክል ስላልመሰለ ብቻ እንደ ፕሮቴስታንቱ ድርቅ ብሎ ይሄን አልቀበልም ዓይነት አካሄድ ማላመድ። ለእኛ ትክክል የማይመስለንን ነገር ትክክል አይደለም ማለት ከጀመርን ከመጽሐፍ ቅዱስ የሚቀረን ምንም ነገር አይኖርም። ይህ አገላለጽ ይጸናል ይቀየር ከማለት ይልቅ አረዳዱን ማላመድ የተሻለ ነው። እንዲያ ካልኾነ "ንባብ ይገድላል ትርጓሜ (መንፈስ) ግን ሕይወትን" ይሰጣል መባሉ ለከንቱ ኾኗልን? በአዋልድ መጻሕፍት ያሉ ጸነን የሚሉ ቃላትን በአጠቃላይ ከማነወር በደንብ አጥንቶ ንባቡ ከጥንት ነበረ ወይስ አልነበረም? መልእክቱ ምንድን ነው? መቼ ተጻፈ? በተጻፈበት ጊዜ ያን ቃል ሰዎች እንዴት ነበር የሚረዱት? ሥርዋጽስ ነው ካልን ምን ያህል ምርምር አድርገን አረጋግጠናል? መሰል ጥያቄዎች በእርጋታ ሳይመለሱ በድፍረትና ኹሉን ዐውቃለው፤ በኹሉም ቦታ አስተያየት እሰጣለው የማለት ክፉ መንፈስ የክፉ ልምምድ ውጤት ነው።

5) ትችትን መጥላት የብዙዎቻችን ችግር ይመስለኛል። የሚተቹን ሰዎችን በሰበሰብናቸው ድጋፊዎች ማስጠቃት። ራስን አይነኬ አድርጎ ለማቅረብ በሥነ ዘዴ መጣር። ምንም ነገር ይኹን እኛ ስንለው ትክክል ነው ብሎ ትክክለኝነትን በራስ ልክ ሰፍቶ የመዝጋት ዝንባሌ። በቃ እንት ካለ አለ ነው! ወዲህ ወዲያ የለውም ብሎ የራስን አስተያየትም ኾነ አንዳች የኾነ ነገር ምሰሶ አድርጎ የማቆም ክፉ ፍላጎት። ሰወር ያለ ራስን Infallible የማድረግ ዝንባሌ መጨረሻው ጥፋት ነው። ለማንም ሰው ቢኾን ይህ ጎጂ መኾኑን ምእመናንም ልብ ልንል ይገባል። እኛ ሰዎች ነን እንጂ ያገኘን ኹሉ እንደ ፈለገ አድርጎ የሚመታን ኳስ አይደለንም። ራሳቸውን ሳያውቁትም ቢኾን ማስመለክ ላይ የደረሱ አካላት ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር ሳይኾን በጣም በጥንቃቄና በሥነ ዘዴ ወደ ራሳቸው ይሳባሉ፤ ዋነኛዎቹ የሃይማኖት ተቆርቋሪዎችም እነርሱ እንደ ኾነ አድርገው ለማስቈጠር ይጥራሉ። እንዳይነቃባቸው ደግሞ "እኔ ተራ ሰው ነኝ" ምናምን እያሉ ሙድ ይይዙብናል! አቤት የሚዲያ ሰዎች ድንቍርናችን ያሳዝናል በእውነት። እግዚአብሔር የልቡናን ሐሳብ ያውቃልና ማንጫጫትና መንጫጫት አያስፈልግም፥ ራስን ዝቅ አድርጎ አካሄድን ማስተካከል እንጂ።

6) ሌላው ደግሞ ትችትን የምንወድ መብዛታችንም ክፉ ልምምድ ነው። ማንኛውንም ነገር በኔ ትችት በር በኲል ይለፍ። ማንንም ቢኾን ስሕተት አወጣበታለሁኝ ብሎ የማሰብ ዓይነት እስኪ መስል ትችት ላይ ብቻ ማትኮር። ትችት አስፈላጊ ቢኾንም፤ ማን? እንዴት? ለምን? ይተቻል የሚለውን ማጥራት ግን ያስፈልጋል። ለትችት የማይመጥን ኹሉ የሚተች ከኾነ ትችት የቅናት ውጤት ሊኾን የመቻል ዕድሉ ከፍ ይላል። በቅንነትና በንጹሕ ልቡና ኾኖ በአግባቡ የሚደረግ ትችት ግን ኹሌም ቢኾን የተሠራውን ሥራ የበለጠ የሚያጠነክር እንደ ኾነ ይሰማኛል። በአንድ አካል ላይ አንድ ችግር ስናይ ለመተቸት የምንሯሯጠውን ያህል ለበጎ ሥራውስ ለምን ያን ማድረግ አቃተን ብለን እንጠይቅ። በሌላ በኲል ትችታችን ኹሉ ተቀባይነት ማግኘት አለበት ብለንም የምናስብ ከኾነ ይህም ትክክል ሊኾን አይችልም። እኛ የምንልህን ብቻ ስማ እንደ ማለት ይኾናልና። የራስንም ትችት ኹሌም

ዮሐንስ ጌታቸው

28 Oct, 07:13


ቢኾን እየመረመሩ ስሕተት መኾኑን ሲደርሱበት ይቅርታ ማለትን መልመድ ያስፈልጋል። ይህ ሳይኾን ኹሌ ስሕተት ብቻ ያልነው ላይ ከተለጠፍን ለራሳችን ሕይወትም ጉዳት ነውና ከዚህ ክፉ ልምምድ እንውጣ!


https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

25 Oct, 18:43


💔  ክፉ ቀን 💔  
✍️  ይህቺ  ልጅ ዳግማዊት ሰለሞን በሻሸመኔ ደብረ አስቦ አቡነ ተክለ ሀይማኖት ቤ/ን ሰ/ት/ቤት ውስጥ የምታገለግል የ 18 አመት ብላቴና ናት። ገና ሮጣ ሳትጠግብ የ10ኛ ክፍል ተማሪ እያለች ነው እንደ ቀላል የታየው የእግሯ ህመም አልጋ ላይ የጣላት። ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሀኪሞች ቦርድ ህመሟ "የአጥንት መቅኔ" እንደሚባልና ህክምናውንም በውጭ ሀገር መከታተል እንደሚገባት ቀጥሎም ገንዘቡም 4 ሚሊየን የኢትዮጵያ ብር እንደሚያስፈልጋት ይነገራታል።
  ✍️  አባቷ መቶ አለቃ ሰለሞን አስፋው በውትድርና ከመቆየታቸውም በላይ ለእናት ሀገራቸው አንድ እግራቸውን ሰተው በክራንች የሚሔዱ በጡረታ ደሞዝ የሚተዳደሩ አባት ናቸው። ወሩ ደርሶ ከአስቤዛ ለማይተርፋቸው ሌሎች ማህበራዊውን ህይወት በችግር ለሚመራ ቤተሰብ 4 ሚሊየን እንደ ከባድ መቅሰፍት ነው።
✍️  " እኔ አንዴ አይደለም ለምን አስር ጊዜ አልሞትም ምንም አይመስለኝም። ብዙ ነገር አይቻለሁ። ልጄ ግን መማር ትፈልጋለች እንደ እኩዮቿ ማገልገል ትፈልጋለች መኖር  ትፈልጋለች😭 ቆማ መራመድ ትፈልጋለች ምን አለበት የሷን ለእኔ ባረገው"   አባቷ መቶ አለቃ ሰለሞን በእንባ የሚናገሩት ንግግር ነው።
✍️  ልጄን ከእግዚአብሔር በታች አድኑልኝ የሚለውን የበረከት ጥሪ ሁላችንም በደስታ ተቀብለን አነሰም በዛም ሳንል ለተወሰነ ቀናት በሚቆየው ቻሌንጅ ብንረባረብ ተሰፍሮ ከማያልቀው በረከት ተካፍለን ለእህታችንም እንደርስላታለን።  ይሔ  1000372941549  የአባቷ መቶ ሰለሞን አስፋው አካውንት ነው። የምታስገቡ እህት ወንድሞች ለማስተማርያነትና ለቁጥጥር ያመቸን ዘንድ አስገብታችሁ ስሊፑን በውስጥ መስመር ላኩልን።  ሁላችንም በምንችለው እንሳተፍ። የማንችል ደግሞ ሌሎች ወንድሞች እንዲመለከቱት ሼር በማድረግ እህታችንን ለመርዳት እንተባበር።

ዮሐንስ ጌታቸው

23 Oct, 05:02


ይህንን ትምህርት በዚህ ቻናል ውስጥ ያላችሁ እኅት ወንድሞቻችን ኹላችሁም ስሙት። ለሌሎች እኅት ወንድሞቻችሁ Share በማድረግ አድርሱት።

https://youtu.be/3TJjaUUIk60?si=MROUxDY-GTGoRe-K

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

22 Oct, 04:28


#የዛሬ_ገጠመኝ#

ትንትና ማታ አዳማ አቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን ጉባኤ ኖሮኝ ከአዲስ አበባ ወደ አዳማ ሄድኹኝና እንዳቀርብበት በተሰጠኝ ርእሰ ጉዳይ በጣም በአጭሩ አቀረብኹኝ። አስቀድመው እዚያው እንዳድር አመቻችተውልኝ ስለ ነበር፤ አድሬ ካደርኹበት ቦታ ሌሊት 11፡30 ተነሥቼ ተዘገጃጀኹና ወጣኹኝ። ካደርኹበት ወደ አዲስ አበባ ለመመለስ የአዲስ አበባ ሚኒ ባሶች ወዳሉበት መናኸሪያ መሄድ ነበረብኝ። ስለዚህም ኹለት ሰው የያዘ ባለ ባጃጅ ታክሲ እየፈለግኹ መሄዴን ገምቶ መናኸሪያ ነህ አለኝ፤ አዎን አልኹኝ። አቆመልኝ አንደኛው ተሳፋሪ ከባጃጁ ወጥቶ በቅርብ ስለምወርድ ብሎ ከመሐል አስገባኝ። መሐል መግባት ባልወድም እሺ ይኹን ብዬ ገባኹኝ።

ጉዞ ወደ መናኸሪያ ተጀመረ። እየሄድን ነው! ትንሽ ሄድ እንዳልን ልወርድን ነው ያለው ሰውዬ 50 ብር አውጥቶ ለባለ ባጃጁ ይሰጠዋል። ባለ ባጃጁም ዘርዝር አልያዝኹም፥ ዝርዝር ብር ያለው ይኖር ይኾን ይለናል እኔንና አንደኛውን ባጃጁን እየነዳ። እኔም ወደ ቲሴ እጄን ከትሁና በይውህና ኾኜ 40 ብር አለኝ፥ መልሱ ስንት ነው? ልስጠውን? አለኹኝ። በዚያን ጊዜ 10 ብር ብቻ ስጠኝ ይበቃል አለኝ። ሰጠኹት። በዚህ ሂደት በቅርብ ወራጅ ነኝ ያለኝ ሰውዬ በእጁ ቦርሳ ይዟል፥ ኪሩን እንደሚፈታትሽ ኾኖ የኔን ስልክ በጣም በእርጋት ከኪሴ ያወጣል። እኔም የኾነ ስሜት ይሰማኛል! የሻሼ አራዳ ነኝና😂 ስቀልድ ነው ገጠሬ ነኝ! ስልኬን ከኪሴ መውጣቷ ገብቶኛል።

ባለ ባጃጁም ወዳት መናኸሪያ ነህ? ወደ አሰላ ወይስ ወደ አዲስ አበባ ሲለኝ፥ ወደ አዲስ አበባ አልኹት ላካስ ወደ ሌላ መስመር እየወሰደኝ ኖሯል! አትነግረኝምን? እዚህ ውረድና ወደዚያ ሄደህ ሌላ ባጃጅ ያዝ ብሎ የሰጠኝን 10 ብር እንዳዛኝ ኾኖ ይሰጠኛል። እኔም ተቀብዬ ልወርድ ስል ኪሴን ቼክ አደረግኹኛ🙄 ስልኳን አጅሬው ከኪሴ አውጥቷታልና፥ ወንበሩም ላይ ቁጭ ብላለች፥ ቶሎ በፍጥነት ብድግ አድርጌያት ወረድኹላቸው! በአራዶች አራዳ ኾንኹባቸው። እየመረራቸው የሄዱ ይመስለኛል። እንዳወጣኸው ወደ ኪስህ አትከተውም ነበርን? ምን አንቀራዘዘህ? የጠዋት አየራችንን አከሰርኸው? ከኪሴ አውጪው ደግሞ ወይኔ! ምን ዓይነት መርዝ ነው😂 እያለኝ ይኾናል።

ስልኬን ቢወስዷት ስልክ ይገዛል በውስጡ ያስቀመጥዃቸው ዶክመንቶች ግን እጅጉን የሚጠቅሙኝ ናቸው። በዚያ ኀዘን ይሰማኝ ነበር። በዚህ አጋጣሚ ስልኮች ግን ሳያዝኑብኝ አይቀርም። በእጄ ብዙ ዓመት የመበርከት አጋጣሚ አግኝተዋልና። ከ5 ዓመት በታች የቆየ ስልክ ትዝ አይለኝም። አኹን የያዝኹት ግን ገና ኹለት ዓመቱ ነበር😁

ይህ ገጣኝ ምን አመለከተኝ መሰላችሁ፥ ንቍ ካልኾንን ሰይጣን እኛ በምንፈልገው መንገድ ወደ እኛ መጥቶ ወደ ምንሄድበትም የሚሄድ መስሎ የሚያጠቃን መኾኑን ነው። ብዙዎቻችንን በኃጢአት ጣዕም አስምጦ የሚያስቀረን እኛ በምንወደውና በምንመርጠው መንገድ መጥቶ ነው። በእርሱ ቍጥጥር ውስጥ ያስገባን ሲመስለው እንኳን በጥንቃቄና በንቃት የምንጓዝ ከኾነ በእግዚአብሔር ቸርነት ወጥመዱን መስበር እንችላለን። ተስፋ መቍረጥ፣ ትክዝ ብሎ መጨነቅ ወደ ጉዳት የሚያደርሰን እንጂ የሚጠቅመን አይደለም። ዐይነ ልቡናችን የሚሰረቀው ባልተገባ ጭንቀት ውስጥ ገብተን ስንዋኝ ነው። ምንም እንኳን አጋንንት እኛን ለመጣልና ወደ ኀዘን ውስጥ ለማስገባት ቢጥሩ፣ የምንወደውንም ነገር በር አድርገው ቢቀርቡን በጥንቃቄና በንቃት የምንኖር ከኾነ አንወድቅም። እግዚአብሔር አምላካችን አጋንንት ከሚያሴሩብን ክፉ ሴራ ይጠብቀን።

ሌላኛው መልእክት። ምንም እንኳን አዳማ በተደጋጋሚ በጉባኤ ምክንያት ብሄድም ብዙም አላቃትም። እነዚህ ሰዎች የበለጠ እናጥቃው ቢሉ የፈለጉበት ወስደው የፈለጉትን ሊያደርጉብኝ ይችሉ ነበር። ያሳደገኝ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ግን በአምላክ ቸርነት በዕለተ ቀኑ ከዚያ ጠበቀኝ። ይህ ማለት እኛ በማናስበው መንገድ ለጥቃት ራሳችንን አጋልጠን ብንሰጥ እንኳን እግዚአብሔር የሚጠብቀን መኾኑን ነው። አላወቅን ይኾናል እንጂ እግዚአብሔር ብዙ ጊዜ ከክፉ ሴራ ጠላትን እንኳን በእኛ ላይ እንዳይሠለጥኑ ሕሊናቸውን የሚከለክል ቸር አምላክ መኾኑን ልብ እንበል። ክፉ ነገር ከደረሰብን በኋላ ብቻ የሚያድነን ሳይኾን እንዳይደርስብንም አስቀድሞ የሚያድነን አምላክ ኹሌም እናመስግነው። በእምነትና በንጽሕና ኾነንም እርሱ የሚፈልገውን እናድርግ።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

20 Oct, 18:54


++++++#ጠባቧ_መንገድ#++++++

"በተጨባጭ እውነታ ሰፊውንና ልቅ የኾነውን መንገድ ይዘን ሳለ ጠባቡንና የቀጠነውን መንገድ እየተከተልን እንደ ኾነ በማሰብ እንዳንታለል በራሳችን ላይ ቅርብ ትኲረት እናድርግ። ቀጥሎ የሰፈረው ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን እንደ ኾነ ያሳይሃል፦ ሆድን ማጎስቆል (ስስትን መግደል)፣ ትጋሃ ሌሊት (ሌሊቱን ሙሉ መቆም)፣ ጥቂት ውኃ መጠጣት፣ ቍራሽ ዳብ መብላት (ከፊለ ኅብስት)፣ በተዋርዶ ድርቅ መንጻት፣ መናቅ፣ ፌዝን መቀበል፣ መሰደብ፣ የገዛ ፈቃድን ቆርጦ መጣል፣ በሚያስቆጣ ነገር መታገሥ፣ ባለ ማጉረምረም ንቀትን መታገሥ፣ ስድቦችን ቸል ማለት፣ ያልተገባ ጠባይን ጸንቶ መታገሥ፤ ሲታሙ አለመቆጣት፣ ሲዋረዱ አለመቆጣት፣ ሲነቀፉ ትሑት መኾን ነው። የገለጽናቸውን ጎዳናዎች የሚከተሉ ብፁዓን ናቸው፣ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴ 5፡3-13።" እንዲል ዮሐንስ ዘሰዋስው። (ሳሙኤል ፍቃዱ (ተርጓሚ)፣ ምዕራግና ድርሳን፣ 2011 ዓ.ም፣ ገጽ 102)።

በዚህ አባት ጽሑፍ ውስጥ አንደኛ ራሳችንን መመርመር እንዳለብን ተገልጿል። ልቅ በኾነው ሰፊ መንገድ በተባለው የዓለማዊነት መንገድ ላይ መኾን አለመኾናችንን በትኩረት እንድናስተውል ምክረ ሐሳብ ቀርቧል። ኹል ጊዜም ቢኾን ትክክለኛ ወደ ኾነው መንገድ ለመግባት አስቀድሞ የቆምንበትን መንገድ እና በዚያ መንገድ እንድንጓዝ ያደረገንን ውስጣዊ ፍላጎት መረዳት ያስፈልጋል። ምን ያህልስ ጊዜ ልቅ በኾነው የኃጢአት መንገድ ተጉዘን ይኾን? ምን ያህልስ የዚያ መንገድ ጣዕም በውስጣችን ቀርቶ ይኾን? እንዴትስ ከዚያ መንገድ መውጣት እንችላለን። እያልን በእርጋታ ለራሳችን ጥያቄ እያቀረብን ራሳችንን እንመርምር።

ኹለተኛው መሠረታዊ ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን ማለት እንደ ኾነ የተገለጸበት ነው። ጥቂት መመገብን ከመለማመድ ጀምሮ ማንኛውንም ክፉ የተባሉ ነገሮችን የሚያደርጉብንን መታገሥ ተገቢ መኾኑን ያስረዳል። መንገዱን ጠባብ ያሰኘውም፥ የተገለጹትን ነገሮች ለመተግበር እጅግ የሚከብዱ ስለ ኾነ ነው። ጽድቁንና መንግሥቱን እያሰብን የምንኖር ከኾነ ግን ከባድ ሊኾኑ አይችሉም። ጠባቡ መንገድ ጣዕመ መንግሥተ እግዚአብሔርን እያሰቡ ኃጢአትን መጥላትን ማዕከል ያደረገ ነውና። የሚንቁንን፣ የሚሰድቡንን፣ የሚያሙንን መታገሥ ለብዙዎቻችን አስቸጋሪ ነው። በእውነትም የሚጠሉንን ላለመጥላት እየታገልንን ኹሌ ራሳችንን ትዕግሥትን ብናለማምድ እግዚአብሔር ይረዳናል። ትዕግሥት በእኛ ጥረት ብቻ ሳይኾን ከእግዚአብሔርም ጸጋ ኾኖ የሚሰጥም ነገር ነውና። እኛ ከልባችን ክፉን በትዕግሥት ስንቀበል እግዚአብሔር ጽናቱን ይሰጠናል። የጠባቡ መንገድ መድረሻው መንግሥተ እግዚአብሔር መኾኑን በሕሊናችን ውስጥ አስቀምጠን፥ መንግሥቱን እያሰብን እንኑር። አንድ ሯጭ ትኲረቱን በሙሉ የሚያደርገው ቀድመውት ያሉ ተወዳዳሪዎች ላይ እንደ ኾነ ኹሉ እኛም ትኲረታችንን ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር አቅጣጫ ካደረግን በእኛ ላይ የሚደረጉ ክፉ ነገሮችን ኹሉ ሳናያቸው ማለፍ እንችላለን።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

18 Oct, 17:19


ቤቱን በዓለት ላይ የሠራ ልባም ሰው!

ሙሉ ቪዲዮውን ሊንኩን በመጫን ዩትዩብ ላይ ማግኘት ትችላላችሁ ።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://youtu.be/HudBRUiCdCQ?si=Vc32xgpVI7KGwxwp

@MasyasTube

ዮሐንስ ጌታቸው

14 Oct, 14:52


+++++++#በበጎነት_መጽናት#+++++++++

ማር ወግሪስ እንዲህ ይላል፦ "ዳግመኛም ስማኝ ልንገርህ! ለዘለዓለም ላንተ ይብስብሃልና ባደርክበት ኹሉ ቃልህን አትለውጥ። በሰዎች መካከል ጥልን አትዝራ፤ አነዋወርህ ኹሉ በሰላም ይኹን፤ ወደ ልቡናህም ቍጣን አታስገባ፤ ወንድምህ የበደለህን ከቶ አታስብ። የቍጡ ሰው ድካሙ ኹሉ በዐይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ ፈጥኖ ያልፋልና። ቂምን በልቡናው የሚያኖር ሰው የሰይጣን ደቀ መዝሙሩ ነው፤ የዘለዓለም ሕይወትንም አያያትም። ማንንም ማንን አትማ፤ ከማንም ጋር አትከራከር፤ የባልጀራህን ንብረት አትመኝ የሌላውንም አትቀማ።

ሐሜተኛ ሰው የእግዚአብሔር ጠላቱ ነው። በጠላትህ ውድቀትና ሞት ደስ አይበልህ፤ ባዘኑት ላይ አትሣለቅ፤ ለዕውሩ መሰናክል አታኑርበት። ስትጸልይ ለመቀመጥ አትቸኩል፤ ለጸሎት ጽሙድ ኾነህ በቆምክበት ቦታ ኹሉ አትነቃነቅ፤ በመካነ ጸሎትህ ላይ አዘውትረህ ቆመህ ተገኝ። ለለመነህ ኹሉ ስጥ፤ ከሌለህ ደግሞ እግዚአብሔር ይስጥህ ካለው ያድርስህ ብለህ በለዘበ ቃል ተናገር። የምትሠራውን ሥራ ኹሉ ፊት አይተህ አድልተህ አትሥራ። የደረሰብህን ኹሉ እግዚአብሔርን አመስግነህ ተቀበል። ይህንን ያደረግህ እንደ ኾነ በእግዚአብሔር ትእዛዛትና ሕግጋት አንተ በእውነት ፍጹም ነህ። እኔስ በእውነት የእግዚአብሔርን ጥበብ አደንቃለሁ።" እንዲል። (ገብረ ኪዳን ግርማ (አባ፣ የአራቱ ጉባኤያት የምስክር መምህር)፣ መጽሐፈ ወግሪስ፣ 2013 ዓ.ም፣ ገጽ 51)።

የሕይወት መርሐችን ከላይ በተገለጸው መሠረት ቢኾን በበጎ መጽናት እንችላለን። ክፉ ነገር በሕሊናች ውስጥ በመጣ ጊዜ ወዲያው አስወግደን ብናስወጣው እና ሕሊናችን ውስጥ የእግዚአብሔርን ቃል ኹል ጊዜ ብናስቀምጥ፥ በዚያም ቃል ብንመሰጥበት ሕይወታችን የተስተካከለ ይኾናል። ድንገት ስሜታዊ ኾነን ወደ ክፉ ልንሳብ ስንል ራሳችንን የምንቆጣጠርበት የእግዚአብሔር ቃል ውስጣችን ሊኖር ይገባል። በእርግጥም የሕይወት መርሐችንን በቃለ እግዚአብሔር እያደረግን ስንሄድ ስሜታችን በራሱ በቃለ እግዚአብሔር እየተገራ ይሄዳል። ውስጣችንም በቃለ እግዚአብሔር መመራትን እንደ ግዴታ መቀበል ይጀምራል። እንዲህ ሲኾን ብንጣላ ወዲያው ይቅር እንባባላለን፥ ቢበድሉን እንታገሳለን፥ ቢሰድቡን ስድብ የሚገባን ኃጥእ እንደ ኾን አድርገን እንቀበላለን፣ ቢንቁንም የክፉ ሥራችን ውጤት መኾኑን አምነን ያለተቃውሞ እንቀበላለን። እንዲህ በበጎ እየጸናን ስንሄድ የሚረብሸን ነገር በእኛ ላይ ኃይሉን እያጣ ይሄዳል፤ ሕይወታችንም በፍጹም ሰላምና ዕረፍት ይመላል።

እንግዲህ ምክንያታዊ ነኝ ብለን ከምናስበው አጸፋዊ መልስ ኹሉ እየራቅን እንሄዳለን። እንዲህ ያደረግኹት እንዲህ ስላደረገችኝ/ገኝ ነው እያሉ ከመናገር ኹሉ ነጻ እንወጣለን። በሕይወታችን የሚገጥሙንን ችግር የምንላቸውን ነገሮች ኹሉ የመጋፈጥና የማሸነፍ ብርታታችን ታላቅ ይኾናል። የብዙ ዓመታት ሕማም ቢኾን፣ ወይም የገንዘብ እጦት ችግር ቢኾን፣ ወይም ከሰዎች ዘንድ ፍቅር አጣኹኝ ብሎ የማሰብ ፈተናም ቢኾን እንሻገረዋለን። መጀመሪያ መስተካከል ያለበት አስተሳሰብ እና ነገሮችን የምንረዳበት መንገድ ነው። ሲቀጥልም የመኖር ትርጒሙና ዓላማው ግልጽ ኾኖ ሊገባን ያስፈልጋል። ይህ በትክክል ሲገባን ያን መፈጸም ዋና ዓላማችን እየኾነ ይመጣል። ስለዚህ ሰይጣን ሊጥለንና ጥቅም አልባ ሊያደርገን የሚፈጽምብን ጥቃት ኹሉ ይከሽፋል። በበጎነት ጽናታችንም ድል ይነሣል። ስለዚህ ስንኖር ለምንድን ነው የምኖረው? እንዴትስ እንድኖር ነው ፈጣሪ የሚፈልገው? ፈጣሪስ እንደሚፈልገው መኖር ያልቻልኩት ለምንድን ነው? ለመኾኑ በበጎነት ጸንቼ እንዳልኖር የሚከለክለኝ ምንድን ነው? የሚሉ ጥያቄዎችን ለራሴ እየጠየኩ ሕይወቴን እያስተካከልኹኝ ልኖር ይገባኛል። በምን መመሪያ እንዳንል ከላይ ማር ወግሪስ ያስቀመጠልን ድንቅ የሕይወት መመሪያ አለልን።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

10 Oct, 19:44


https://youtu.be/ISLQf-zUAeQ?si=bkgwuu7OEpkuriy6

ዮሐንስ ጌታቸው

08 Oct, 05:59


+++++++#የሰይጣን_ወጥመድ#+++++++

አባ ኔቅጣስ ስለ ኹለት ወንድሞች የሚከተለውን ተናግረዋል። አንድ ጊዜ ኹለት መነኮሳት በአንድነት ለመኖር ወሰኑ። አንደኛው በልቡ "ወንድሜ የሚፈልገውን ኹሉ አደርግለታለሁኝ" ሲል ቃል ገባ። ሌላኛውም "የወንድሜን ፈቃድ እፈጽምለታለሁ" ሲል በልቡ ወሰነ። በዚህ ውሳኔያቸው ለብዙ ዘመናት በለጋሥነት ኖሩ። በዚህ ፍቅራቸው የቀና ሰይጣን ሊለያያቸው ተነሣ። በበኣታቸው በር ላይ ቆመና ለአንደኛው ርግብ ለሌላኛው ቍራ መስሎ ታያቸው። በዚህ ጊዜ አንደኛው መነኩሴ "ርግቧን አየሃት?" ሲለው ሌላኛው ደግሞ "ርግብ አይደለችም ቍራ ናት" ሲል መለሰ። "ርግብ ናት"፣ "ቍራ ነው" ክርክር ጀመሩ። ክርክሩ ወደ ጭቅጭቅ፣ ጭቅጭቁ ወደ ድብድብ አመራና ደም በደም እስኪ ኾኑ ድረስ ተደባደቡ። በመጨረሻም ተለያዩ። ከሦስት ቀናት በኋላ ወደ ልባቸው ተመልሰው ኹለቱም ተፀፀቱ። ይቅርታም ተጠያየቁ። ኹለቱም በተለያየ መልክ አንድ ዓይነት ነገር ማየታቸውንና ልዩነታቸው የመጣው ከነገሩ ሳይኾን ከዲያብሎስ መኾኑን ተረዱ። እስከ ዕለተ ሞታቸውም ድረስ አብረው ያለ ፀብ ኖሩ። (ዳንኤል ክብረት (ዲ/ን፣ አርተር)፣ በበረሓው ጉያ ውስጥ፣ ሦስተኛ ዕትም 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 57-58)።

ብዙ ጊዜ መንፈሳዊ ሕይወታችን ምስቅልቅል የሚልብን በእንዲህ ዓይነት ስውር የሰይጣን ወጥመድ ነው። አንድን ነገር በእርጋታ ከመመርመር ይልቅ ያየነውን ብቻ መሠረት አድርገን ወደ ተሳሳተ ውሳኔ የምንገባም እና የእግዚአብሔርን መግቦት የምንጠራጠር ብዙ ሰዎች አለን። ከሌሎች ጋር በፍቅር ለመኖር የወሰነውን ውሳኔ ድንገት በአንዲት ተራ ምክንያት የምናፈርስ መኾኑን እናስተውል። የገመጠንን ነገር በልቡናችን ከገባነው ቃል ኪዳን ጋር እያስተያየን በትዕግሥት ልንጸናና ረጋ ልንል ሲገባን በጥድፊና ተቃራኒ መልስ እየመለስን ወደ ጥልና ፀብ የምንገባ ልንጠነቀቅ ይገባናል። የልቡናችንን ዐይን ስሜታዊነታችንን አንጫነው፤ እኔ የማየው ብቻም ነው ትክክል ብለንም የሌሎችን ሐሳብ አንግፋ። ለሕይወታችን ሊጠቅም የሚችለውን ወዳጅ እኔ እንደ ማየው አላየም ብለን አንግፋው። በጎ አንድነት እንዳይኖር የሚሻ ጠላት ልዩነትን ኾነ ብሎ እየፈጠረብንም እንደ ኾነ ልብ እንበል። የሚሻለን ኹሌም ቢኾን ራስን ዝቅ አድርጎ ለሕይወት ከሚጠቅመን ወዳጃችን ጋር በአንድነት መኖር ነው። እግዚአብሔር ዓይነ ልቡናችንን ያብራልን።

በሌላ በኩል ደግሞ አንድ ነገር በተለያየ መንገድ ለተለያዩ ሰዎች በማሳየት ሰይጣን ምን ያህል ፀብና ጥልን የሚፈጥር ክፉ ጠላት መኾኑን ልብ ማለት እንችላለን። ክፉው ጠላት ሰይጣን እኛን ለመጣል ያን ያህል የሚዋጋ ከኾን እኛስ እርሱን ለመግጠም ምን ያህል ሠልጥነን ይኾን? ይህን ኹላችንም ለየራሳችን እንጠይቅ። በክርስትና ሕይወት በጣም የዛልን፣ በእምነታችን ላይ ጥርጣሬ የመጣብን፣ በሃይማኖታዊ ጉዳይ ለዘብተኛ ወደ መኾን እየሄድን ያለን በሙሉ ለአንድ አፍታ ቆም ብለን እናስብ። ጠላት ምን ያህል የጥፋት ጉድጉድ እየቆፈረልን እንደ ኾነም ልብ በማለት ንቁ ተዋጋጊ እንኹን። ሊዋጋው እና ሊያጠፋው በብዙ ኃይል ታጥቆ የሚመጣን ጠላት እያየ ባዶ እጁን ቍጭ ብሎ የሚጠብቅ ተዋጋ ይኖራልን? ቢኖሩ እንኳን ለማሸነፍ ያሰበ ሳይኾን አስቀድሞ በስንፍናው ምክንያት የተሸነፈ ጠላትም ሲመጣ እጁን ሰጥቶ ባርያ ሊኾንለት ያቀደ ብቻ ነው ሊኾን የሚችለው። ወይም ሕይወቱን የጠላና ለበለጠ ሥቃይና መከራ ራሱን በፈቃዱ አሳልፎ ለመስጠት የፈቀደ ሞኝና ሰነፍ ነው ሊኾን የሚችለው። ይህ ደግሞ በራስ ላይ ራስን ጠላት እንደ ማድረግ ነው። ስለዚህ በጥንቃቄ እንኑር።

ሰይጣን በተለያየ መልክ እየተገለጠ ወደ ልዩነትና ፀብ የሚወስድ መኾኑን ልብ ከማለት ጋር እኔ የማየው ብቻ ነው ትክክል ከማለት በፊት ጸሎት ማድረግ ወደ እግዚአብሔር መጮህ ያስፈልጋል። ብዙ ጊዜ ልዩነት እየመሰሉን የምንጣላባቸው ነገሮች ልክ እንዲሁ ናቸው። ወደ ልዩነት፣ ፀብና ክርክር፣ አለፍ ሲልም ወደ ጭቅጭቅ እና ድብድብ ድረስ የሚያደርሰን ለነገሮች ያለን የተቃረነ አረዳድ ነው። ኹላችንም ማንኛውንም ነገር በጸሎትና እግዚአብሔርን በመጠየቅ ብናደርገው እጅጉን ጠቃሚ ነው። ተቃራኒ የሚመስለን ወደ ፀብ ሊያመራን የሚችል ነገር ኹሉ የጠላታችን የዲያብሎስ ወጥመድ መኾኑን ኹሌም ልብ እንበል። የእኔ ብቻ ትክክል ነው፣ ያንተ ትክክል አይደለም እያሉ የሌሎችን ሐሳብም ኾነ ንግግር ለማድመጥ ፈቃደኛ አለመኾን ወደ ጭቅጭቅና ከዚያም አልፎ ደም እስከ ማፋሰስ ድብድብ የሚያደርስ መኾኑን ልብ ይሏል። እንዲህ ዓይነት የልዩነትና የፀብ ፈተና በገዳም እንኳን የማይቀር መኾኑን ኹል ልብ እንበል። ስለዚህ አንዱ እሳት ሲኾን ሌላው ውኃ፣ አንዱ ቍጡ ሲኾን ሌላው በራድ፣ አንዱ ቸኳይ ሲኾን ሌላኛው ረጋ ያለ ትዕግሥተኛ መኾን አለበት። ዕለት ቀንና ሌሊት እንደሚኖረው ሕይወትም ብርሃንና ጨለማ ይኖረዋል። ጨለማ ብቻ ቢኾን ወይም ብርሃን ብቻ ቢኾን አኹን ባለን አኗኗር ጥሩ አይኾንም ነበር። እንቅልፍም ንቃትም ያስፈልጋሉና። አንዱ ሲተኛ አንዱ ካላነቃ፣ አንዱ ሲስት ሌላኛው ካላቀና እንዴትስ ሕይወት ሥምረት ሊኖራት ይችላል?

ኹለቱ መነኮሳት ለጊዜው ባይረዱትም ዃላ ወደየልቡናቸው ሲመለሱ ያጣላቸው ሰይጣን እንደ ኾነ ተረድተው፡ ይቅር ተባብለው፡ አንዴ አለያይቷቸው ደም ያፋሰሳቸውን ጠላት እስከ ሞታቸው ድረስ ተዋግተው ድል አድርገውት እነርሱ በፍቅር በአንድነት ምድራዊ ሕይወታቸውን አጠናቀዋል። እንግዲያውስ እኛም እንደነርሱ ወደየ ልቡናችን ተመልሰን የተጣላን ይቅር ብንባባልና ወደ ልዩነት እና ፀብ የመራን ሰይጣን መኾኑን ተረድተን በፍቅርና ክርስቲያናዊ በኾነ አንድነት ብንኖር አሸናፊ መኾናችን በዚያ ይታወቃል። እግዚአብሔር ለኹላችንም ንጹሕ ልቡና አድሎ በፍቅር በአንድነት የምንኖርበትን ኃይል ይስጠን፤ አሸነፍኩ ተሸነፍኩ ከሚያስብል ክፉ እልህና ግራ መጋባት ይሰውረን፤ በእርሱ ቃል ልቡናችን ተሸንፎ ራሳችንን ከኹሉ የምናንስ አድርገን ለመቍጠርም ያብቃን አሜን።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

02 Oct, 05:19


የቱ ይበልጣል?

አንድ እውነተኛ ክርስቲያን ለሦስት ሠራተኞች በቤቱ ውስጥ የቀን ሥራ ሰጣቸው። ሠራተኞቹ ሥራቸውን በጨረሱ ጊዜ ይሸልማቸው ዘንድ ጠራቸው። ታዲያስ ከፊታቸው ሦስት የወርቅ ሳንቲምና ሦስት መንፈሳዊ መጻሕፍትን አስቀምጦ፥ የወርቅ ሳንቲሙን ወይም መጽሐፉን እንዲመርጡ ነገራቸው።

ሁለቱ ሠራተኞች ወዲያውኑ "በበጋ እንጨት እንገዛበታለን" እያሉ የወርቅ ሳንቲሞችን ወሰዱ። ሦስተኛው ሠራተኛ ከፊቱ ያለውን መጽሐፍ አንሥቶ "ዐይነ ሥውር እናት አለችኝ ምሽት ምሽት ላይ ከዚህ መጽሐፍ የኾነ ነገር አነብላታለሁ" እያለ ወሰደ።

ሃይማኖተኛው ክርስቲያንም ፈገግ አለበትና እባክህ የመጽሐፉን የመጀመሪያውን ገጽ ከፍተህ ምን እንደ ተጻፈበት አንበብ አለው። ወዲያውኑ ሠራተኛው መጽሐፉን ሲከፍት፥ ባየው ነገር ተደነቀ ሦስት የወርቅ ሳንቲም በመጀመሪያው ገጽ ላይ ተጣብቆ ነበርና።

ከዚያን እውነተኛው ክርስቲያን ሦስቱን ሠራተኞች እንዲህ አላቸው "ስሙ፤ ምድራዊ ቁሶች መልካሞች ናቸው። ነገር ግን ዘለዓለማዊ ቁሶች የበለጠ መልካሞች ናቸው። ዘለዓለማዊ ነገር የሚፈልግ ሁሉ ምድራዊውን ነገርንም እንደማያጣ ዕወቁ። ክርስቶስ እንዲህ ብሏልና " እናንተስ አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፤ ሌላው ሁሉ ይጨመርላችኋል።" ማቴ ፮፡፴፫። (Orthodox parables and short history)

ይህ ታሪክ አሁን ያለነውን አብዛኛዎቻችንን የሚመለከት ይመስለኛል። ብዙዎቻችን የምንሠራው ምድራዊ ነገር ለማግኘት ብቻ ብለን ነው። ሌላው ቀርቶ ድርጊታችን ዓለማዊ ኾኖ እንኳን የሚያጸድቅ ሽልማት ሲቀርብልን አንፈልግም እንላለን። ምርጫችን በተራ ኃላፊ ነገር ላይ ብቻ የተመሠረተ ነውና። እሳትና ውኃ ቀርቦልን ምረጡ ስንባል ልቡናችን የሚከጅለው እሳት የተባለውን ዓለማዊ ሥራ ለመሥራት ብቻ ነው። ጾምና ምግብ በምርጫ ቀርቦልን ጾምን ትተን ምግብን ብቻ በመምረጥ ሆዳም የኾን ጥቂት አይደለንም። መጽሐፍ ቅዱስና ተራ የዚህ ዓለም ልብ ወለድ ቀርቦልን ወዲያው የምንመርጠው ልብወለዱን ነው። ይህ እንግዲህ በምን ያህል ርቀት የክርስትናን ጉዳይ ሳንረዳ እንደቀረንና ሕይወታችንም እውነተኛ የሕይወትን ትርጒም ትታ ፍሬ አልባ እንደ ኾነችብን አመልካች ነው።

ከክርስትና መከራ እና ከዓለማዊ ደስና የቱ ይሻላችኋል ተብሎ ምርጫ ቢቀርብልን የሁላችንም ምርጫ ደስታን ማግኘት ነው። ምክንያቱም በመከራ ውስጥ የሚገኘውን የማይመረመር ደስታ አናውቀውምና። ሕይወትና ሞት ቀርቦልን የምንመርጠው ሞትን ነው። ይህም ማለት የሞትን ሥራ በጣም እንወደዋለን የሕይወትን ሥራ ግን ፈጽሞ እንጠላለን። ፖለቲከኛው በፖለቲካው፣ ነጋዴው በንግዱ፣ ሠራተኛው በሥራው የሚመርጠው የቱን ነው? ፍትሐዊነት የጎደለውን የሞትን ሥራ አይደለምን?

ከፍቅረ እግዚአብሔርና ከፍቅረ ዓለም በእኛ ዘንድ የቱ ይበልጣል? በዕለት ተዕለት የሕይወት መርሐችን ውስጥ ፍቅረ ዓለም እጅጉን ሠልጥኖብናል። ዓለማዊ ፊልሙ ውስጥ ያለው ፍትወት፣ በመጠጥ ውስጥ ያለው ስካር፣ በዘፈን ውስጥ ያለው ጭፈራ፣ መቀባባቱ፣ አለባበስን አጋንኖ የተለየ ለመምሰል መሞከሩ፣ ታምራላችሁ መባሉ በጣም የሚጣፍጥ ይመስለናል፤ ኾኖም ፍቅረ እግዚአብሔርን ምን ያህል ጣፋጭ እንደ ኾነ ለመረዳት ትንሽ እንኳን ጥረት አናደርግም። በእርግጥ ለመቅመስ ብንጥር ያ ሁሉ ነገር የማይጠቅም መኾኑን እንረዳ ነበር! ስለዚህ የቀረቡልንን ምርጫዎች በእርጋታ እንመርምር፡ የበለጠውን ትተን ወደሚያንሰው አንጓዝ። በጽድቅ ውስጥ እኛ ይበቃናል የምንለው ሳይኾን እግዚአብሔር ያስፈልጋችኋል የሚለውን ሦስት የወርቅ ሳንቲም ሳያስቀምጥልን መቼም አይቀርም። ሌላው ቀርቶ እኛ በምንመርጠው ዓለማዊነት ውስጥ ከምናገኘው አንድ ሳንቲም የሚበልጥ ወደ እግዚአብሔር ስንሄድ ለምድራዊ ኑሯችን ስንኳን ሦስት እጥፍ ይሰጠን ነበር።

ክርስቶስ በመስቀል ላይ የከፈለልንን የፍቅር መሥዋዕትነት ከማስታወስ ይልቅ የዚህ ዓለም ኃላፊ ታሪኮችን ብቻ በማስታወስ አእምሯችንን ያደካከምን ስንቶች ነን? ከወንጌል ይልቅ የፊልም አክተር በሕልማችን የሚመጣብን፣ ከመዝሙር ይልቅ ዘፈን ከአፋችን የሚፈስ፣ ከመንፈሳዊ ጥበብ ይልቅ ዓለማዊ ድንቍርና የሚስማማን፣ ከትሕትና ይልቅ ትዕቢት የሚያንቀን ስንቶች ነን? እንግዲህ የወርቁን ወርቅ መጽሐፍ ቅዱስን ትተን በምድራዊ ወርቅ የተመሰሉትን ዓለማውያት መጻሕፍትን ብቻ በማንበብ የተጠመድን ክርስቲያኖች የቆምንበትን እንመርምር። ለዴማስ በምርጫ ቅዱስ ጳውሎስ እና ተሰሎንቄ ቀርበውለት ነበር፥ ዴማስ ግን የተወደደውን ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስን ትቶ ተሰሎንቄን መረጠ። ተሰሎንቄ ውጫዊ መልኳ የዴማስን ልብ ማረከው። እንግዲህ እኛም እንዲሁ ነው እያደረግን ያለነው። በሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ የተመሰለች ወንጌልን ትተን ኀላፊ የኾነች የዚህ ዓለም ጣዕምን ወደናልና። ለጊዜው ምርጫችን ልክ ይመስለናል፥ ኾኖም የእግዚአብሔር ቃል የተጻፈበትን ቅዱስ መጽሐፍ ትተናል። የችግሮቻችን ኹሉ ምንጭ አመራረጣችን ላይ ነው ያለው። ምርጫችን ካልተስተካከለ ሕይወታችን ጨለማ ውስጥ ይኾናል።

ወደ ትዳር ሕይወት የሚጓዙ አካላትም፡ ሊያገቡት ያሰቡትን አካል ከእምነታቸው አስበልጠው ይመርጣሉ። እምነቱ ርቱዕ ወይም ቀና ኦርቶዶክሳዊ አለመኾኑን እያወቁ፡ እምነቱን ትተው እርሱን ይመርጣሉ። ለዚህም የተሳሳተ ምርጫቸው የየራሳቸውን የመከላከያ ምክንያት ያዘጋጃሉ። ምርጫቸው ልክ እንዳልኾነ እንዲነገራቸው ፈጽሞ አይፈልጉም። ስለዚህ እነዚህ አካላት ስለ ሃይማኖታቸው በፍጹም ልልነት ውስጥ ኾነው ሳለ ጠንካሮች እንደ ኾኑ አድርገው ለማሳየት ይፈልጋሉ። ነገሮችን ኹሉ በራሳቸው ስሜትና ግለ ምልከታ እንዲታይ ይፈልጋሉ እንጂ እንደ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዲታይ አይፈልጉም። ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ወደ እነርሱ እንዲወርድ ይፈልጋሉ እንጂ እነርሱ ወደ ሥርዓቱ መሄድ አይፈልጉም። ይህ በእጅጉ ያስገርማል። ኦርቶዶክሳዊት ሃይማኖታችን ወርቅ ያለበትን መጽሐፍ ቅዱስን ትምስላለች። ከላዩ ሲታይ ወርቆቹ አይታዩም፥ ስለዚህም ዓለማውያን ብዙም አይመርጡትም። ኾኖም ግን ውስጡ ለሥጋ ሕይወታችን የሚያስፈልጉ ወርቆችም አሉት። ስለዚህ ዕይታችንን እናጥራ፡ እውነተኛውን የክርስትና ሕይወት ምርጫ እንረዳ። ከእኛ ስሜትና መረዳት ይልቅ እግዚአብሔርን ከልብ ለመስማት እንዘጋጅ፤ የየዕለት የሕይወት ምርጫችንን በፈቃደ እግዚአብሔር መሠረት ላይ እናቁመው። እግዚአብሔር የሚወደውን ፈቃድ ትተን ለምድራዊ ሕይወት ምቾት ብቻ ስንል የተቅበዘበዝንበት ጊዜ ይበቃል። የእውነት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ማድረግ እንጀምር። እግዚአብሔር በቸርነቱ ዐይነ ልቡናችንን ወደ እውነተኛ ምርጫ ይምራልን።


እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ምልጃ ይርዳን አሜን!

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

30 Sep, 19:10


++++++#ኦርቶዶክሳዊ_ኑሮ#++++

"ሁል ጊዜም በተወሰነ ሰዓት የመንቃት ልምድ ይኑርህ። ምክንያተኝነትን ከአንተ አስወግድ። ከሰባት ሰዓት በላይ የእንቅልፍ ጊዜ አይኑርህ። ከእንቅልፍህም በነቃህ ጊዜ የተሰቀለውን ጌታችንን በመስቀል ላይ እንዳለ አድርገህ አስብ። ራስህን በብርድልስ ሙቀት አታታል። ከመኝታህ አፈፍ ብለህ ተነሣ። ለጸሎት ስትዘጋጅ ወገብህ የታጠቀ መብራትህ የበራ ይኹን። የጸሎት ልብስህን ልበስ። ይህ ጊዜ የዝግጅት ጊዜ ነው። በሠራዊት ጌታ በልዑል እግዚአብሔር ፊት ልትቆም መኾንህን አስብ። ሁል ጊዜም አእምሮህ የአባትህን የአዳምን የእናትህን የሔዋንን ውድቀት ያስታውስ። አምላክህን የሚያስብ በጎ ሕሊና እንዲኖርህ አባትህ አዳም ተጠልፎ በወደቀበት የሥጋ ሐሳብ፣ የሥጋ ኃጢአት ተጠልፈህ እንዳትወድቅ ፈጣሪህን ለምነው። በፊቱ የምትቆምበትን ጸጋ ብርታት እንዲሰጥህ ለምነው።

... በሕመምህ ጊዜ መጀመሪያ በእግዚአብሔር ታመን፥ አዘውትረህ የጌታ ሥቃይ ይታሰብህ። ሥቃይህንና ሕመምህን ያሥታግስልህ ዘንድ የምታውቀውን ጸሎት ያለማቋረጥ ጸልይ። በሕይወት ዘመንህ ሰላማዊና የተረጋጋ ሕይወት እንዲኖርህ ከፈለግህ ሕይወትህን ሊታመን ለሚችለውና አደራውን ለመጠበቅ ለሚቻለው ለእግዚአብሔር አስረክብ። ራስህን ለእግዚአብሔር አሳልፈህ መስጠት ካልቻልክ ፍጹም የኾነ መረጋጋትን አገኛለሁ ብለህ እንዳታስብ። ፍቅር የሚገባውን አምላክህን ውደደውና በፍቅር ኑር። (ታደለ ፈንታው (ዲ/ን)፣ መክሊት፣ 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 90-99)።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

26 Sep, 07:11


++++#ለሚፈሩህ_ምልክትን_ሰጠሃቸው#+++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

+==+++++==+==+++++=++=++
መዝ 60፥4 ላይ ልበ አምላክ ዳዊት “ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠሃቸው" በማለት የተናገረው በምሥጢር ክርስቶስ የሚሰጠንን የሐዲስ ኪዳን ልዩ ምልክት ሲያመላክት ነው። እግዚአብሔር የሚሰጠንን ልዩ ምልክት ገንዘብ ለማድረግ አስቀድመን ሊኖረን የሚገባው “ፈሪሐ እግዚአብሔር" ነው። ፈሪሐ እግዚአብሔር ወደ ጽድቅ መግቢያ በር ስለ ኾነ ልዩ ምልክትን ከእግዚአብሔር ለማግኘት የግድ የፈሪሐ እግዚአብሔርን ልብስ ውስጣችንን ማልበስ አለብን። ያ ልዩ ምልክት ቅዱስ መስቀሉ ነውና! መስቀል ዓለምን በሙሉ አምላካችን ክርስቶስ ወደ ራሱ የሳበበት የሰላም ዓርማ ነው። ይህ ምልክት ክርስቶሳውያን የመኾናችን ዋና መለያ ነው።

=++=+=+=+==+=++=++=+=+=+
እግዚአብሔርን የማንፈራ በፊቱ ቆመን የምንተቻች፣ እርስ በእርሳችን የምንናናቅ እንዴት ምልክቱን ልናገኝ እንችላለን? በፈሪሐ እግዚአብሔር ውስጥ እስካልኖርን ድረስ ምልክቱን ማግኘት አንችልም። ለሚሳለቁበት፣ መቅደሱን የሳቅና የስላቅ ስፍራ ለማስመሰል ለሚጥሩ፣ ትሕትና ለሌላቸው፣ ቅዱሳን መላእክት በመንቀጥቀጥ የሚያመልኩትን አምላክ በመቅደሱ ተገኝተው የሚተኙበት ሰዎች ምልክቱን አያገኙትም። “ለሚፈሩት" ሲል ለሚያመልኩት ማለት ነው። እናመልክሃለን ብለው በተግባር ግን ፈጽሞ የራቁ ሳይኾን በእውነት የሚያምኑበት ናቸው ልዩ ምልክትን የሚያገኙት። ወደዚህ ምልክት ውስጥ በፍቅር እስካልገባን ድረስ ፍቅርንና ሰላምን ገንዘብ ማድረግ አንችልም። በተግባራዊ ሕይወታችን ውስጥ የቀበርነውን መስቀል በንጹሐን መምህራን በኩል ቆሻሻውን አስነሥተን መስቀሉን እስካላወጣነው ድረስ መስቀል የሕይወት ምልክት ነው ብለን የምንፈክር እንጂ በእርግጥም መኾኑን በሕይወት መግለጥ ያቃተን ግብዞች መኾናችንን እናረጋግጣለን።
++=++==++==+++==++=++++=

ምልክት (Banner) የሚያመለክተው አምላካችን ክርስቶስ ዓለምን ለማዳን አንድ ጊዜ የገባበት መቅደስ የተባለውን ቅዱስ መስቀልን ነው። መስቀል ለክርስትናችን መለያ ምልክት ነው። ክርስትናን ከመስቀል ነጥሎ ለማየት መሞከር ማለት ቤተክርስቲያንን ከክርስቶስ ነጥሎ ለማየት እንደ መፈለግ ነው። መስቀል የቤተክርስቲያን ሙሽራ ክርስቶስ ቅድስት ቤተክርስቲያንን በደሙ ሲያጭ ፥መታጨቷን ለመግለጽ ያኖረላት ምልክት ነው። ቤተ ክርስቲያን ጉዞዋ በሙሉ ወደ ድኅነት የሚመራ ነው። በምድር ላይ በምእመናን ልብ ውስጥ መስቀል እየሳለች ሰማያዊቷን መንግሥት ታጓጓናለች።
=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+

መስቀልን በአንገታችን ላይ ማድረጋችን የክርስቶስ ሙሽሪቶች መኾናችን ይታወቅ ዘንድ ነው። አንዲት ሴት ከታጨች በኋላ ሌላ ወንድ መፈለግ የለባትም፤ ሌላም ወንድ እንዲፈልጋት የሚያደርግ ሥራ መሥራት የለባትም። ቤተክርስቲያን መስቀሉን ከክርስቶስ በምልክትነት ከተቀበለች በኋላ ሌላ ነገር አትፈልግም። መስቀል የሕይወቷ ዓርማ አድርጋ ስትታወቅበት ትኖራለች እንጂ። መስቀል በምድር ያለችው ቤተ ክርስቲያን የሚደርስባትን መከራ የሚያመለክት ነው። መከራ ደግሞ የክርስትና ሕይወት መልክ ነው። ብዙዎቻችን የዚህ መሠረታዊ ሐሳብ ተቃራኒ የኾነ ሕይወት ነው ያለን። ከክርስቶስ መከራ ይልቅ የዘፋኞች ዘፈን ልባችንን የማረከብን፤ ከክርስቶስ ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም ይልቅ የዚህ ዓለም ተራ መብልና መጠጥ የሚያረካን ከክርስትናው እውነተኛ መንገድ እጅግ የራቅን ነን። ስለዚህ ምልክቱን ስንተው አጋንንትም መጥተው አደሩብንና ከሙሽራው ፈቃድ ለዩን።

+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=+=++
ምልክት የተባለው በቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ “የክርስቶስ ደም" ነው ይላል። በእርግጥ ይህን ደም ምልክት አድርገን የምንኖር ከኾነ ጠላት ድል ያደርገን ዘንድ አይችልም። መስቀል ደግሞ በዚህ ትርጒም የምልክት ምልክት ነው። የክርስቶስ ደም የፈሰሰበት የሕይወት ዕፀ ነውና። በመስቀል ላይ የተቆረሰውን የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋ የፈሰሰውን ክቡር ደም እናይበታለን። መስቀሉን ስንስም የምንስመው ዕፅነቱን ብቻ አይደለም ይልቅስ በዚያ ላይ ከሞት የሚያድነን ንጹሕ የክርስቶስን ደም ነው። ስለዚህ በመስቀል ዐይንነት ክርስቶስን እናየዋለን። በምልክቱ በኩል ምልክቱን የሰጠንን አምላክ ደሙን ሲያፈስልን ተመልክተን ፍቅሩን እናደንቃለን።

=+=+=++=++++==+===+==+++

“ለሚፈሩት ምልክትን ሰጠሃቸው" የተባለውን ብዙ ሊቃውንት የእስራኤላውያን በኲር በግብጽ ምድር የተረፈበትን የፋሲካውን በግ ደም ነው ይላሉ። ያ ምንም የማያውቀው በግ ደሙ በቤቱ ጉበን ላይ በመቀባቱ ምክንያት የእስራኤል በኩራት ከዳኑ ሕያው በግ ክርስቶስ ቤት አድርጎ በቀራኒዮ በገባበት መስቀል ላይ ባፈሰሰው የሚናገር ደም'ማ እንዴት የበለጠ ድኅነት ይገኝ ይኾን? በኩራችን ክርስቶስን ከልባችን ውስጥ ለማጥፋት የሚተጉትን ክፉ አስተሳሰቦች በሙሉ እንዋጋቸው። ኹል ጊዜም ነገረ መስቀሉን ምልክት አድርገን የአጋንንትን ሐሳብ እናርቅ፤ በእግዚአብሔር ቃልም መሠረት ሳንሠቀቅ መከራ መስቀሉን ለመሸከም እንትጋ። የእውነት መኖር ከጀመርን ሕይወታችን በራሱ የመስቀል ሕይወት ይኾናል፤ ብዙ ግራ የተጋቡ ሰዎችንም የመሰቀል ሕይወትን ጣዕም አቅምሰን ከስሕተታቸው መመለስ እንችላለን። በመኾኑም ምልክታችንን ከጥልቅ ውስጣችን ሕያው አጥር አበጅተን መጠበቅ አለብን።

“እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሳችሁ"

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

21 Sep, 20:21


ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው || (አቤል እና ቃኤል) ወንድምህ አቤል ወዴት ነው?
https://youtube.com/watch?v=uDULKeHpZ_o&si=Kwq35tIClKd8fj7A

ዮሐንስ ጌታቸው

21 Sep, 04:10


++++++++#ግብዝነት#+++++++++

ግብዝ ሰው (አስመሳይ ሰው) በድብቅ እግዚአብሔር የለም ብሎ የሚያምን ነው፤ እግዚአብሔር አለ ብሎ የሚያምን ቢኾን ኖሮ፣ እርሱን ፊት ለፊት ለማታለል ባልደፈረ ነበር። REFERENCE A Puritan Golden Treasury, compiled by I.D.E. Thomas, by permission of Banner of Truth, Carlisle, PA. 2000, p. 151። በሕይወታችን አስመሳይነትን ለብሰን የምንኖር ከኾነ አኗኗራችን ድራማ ይኾንብናል። የሚኾነውና እንዲኾን የምንፈልገው እርስ በእርሱ ይምታታብናል። መልካም መባል እጅግ የምንፈልግና በሰዎች ዘንድም እንደዛ እንድንባል የሚያደርጉ ነገሮችን በማስመሰል የምንተውን፡ ከእውነተኛ የመልካምነት ሕይወት ግን ፈጽሞ ራቅ ያልን ጥቂት ሰዎች አይደለንም።

ግብዝነት ተግባራዊ የኾነ የመጠራጠር ሕይወት ነው። እግዚአብሔርን በአንደበታችን ላንክደው እንችላለን፣ በሕይወታችን ውስጥ ሰዎች እርሱን የምናመልክ አድርገው እንዲያስቡ አድርገን ልንተውን እንችላለን፡ በድብቅ ወይም በስውር በውስጣችን ያለው ግን ድፍረትና ትዕቢት፡ ራስን ማክበር ስለ ኾነ እግዚአብሔር ከሚፈቅደው ውጪ ኾነን እንገኛለን። የዚህ ኹሉ መነሻው ከእውነት መንገድ መውጣትና እውነትን በተግባራዊ የሕይወት ክፍላችን ውስጥ መግፋታችን ነው። ለዚህም ነው ሕይወታችን ከጥፍጥና ይልቅ ምሬት እንዲስማማው ያደረግነው።

መልካም የኾነው እርሱ በአርአያውና በአምሳሉ ፈጠረን እኛ ግን በፈቃዳችን ጥመት ምክንያት ሌላ አርአያን ተላበስን። ውስጣችንን በዚህ ዓለም ፍቅር አሰከርናት፥ የእግዚአብሔር የኾነውን በጎ ነገር ከተግባራዊ ሕይወታችን አራቅነው፥ ራሳችን ላይ በክፉ ዝንባሌያችን ምክንያት የዝሙትን እሳት አነደድን። ራሳችንም ባነደድነው የዝሙት እሳት ተቃጠልን፣ ረከስን፣ ቆሸሽንም፤ ኾኖም በሰዎች ዘንድ ንጹሕ አድርገን ራሳችንን በማሳየት ጻድቅ ተሰኘን፥ ይህ በእጅጉ አስገራሚ ነው።

ግብዝነታችን ከማደጉ የተነሣም፥ ግብዝ መኾናችንም ተረሳን፥ ውስጣችን በከንቱ ውዳሴ፥ በዚህ ዓለም ክብር ገነነች። ሰዎችን ከሰዎች አበላለጥን፥ ፍትሐዊነትን ከአእምሮችን በግብዝነታችን ብሩሽ አጠብናት፥ ፍትሕ ርትዕ የምትመስል ሌላ አዲስ ነገር አበጃጀን። ስለዚህም የማንሰማ፥ የማናስተውል፥ አፍቅሮተ ሰብእ የሌለን፥ በራስ ወዳድነት ጽናት የታጠርን፥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ለዓለም የተመቸን፥ በውስጣችን ፈጽሞ የረከስን፥ ወደ እውነተኛ ሕይወት የመመለስ ፍላጎትና ወኔያችን የሞተብን ስንት ነን? እጅግ ብዙ! እግዚአብሔር በቸርነቱ ዓይነ ልቡናችንን ያብራል።

መፍትሔውም ወደ እውነት ለመመለስ ኹል ጊዜ ሳያቋርጡ መትጋት ነው። እውነት የምትሽሞደሞድ አይደለችም፥ በግል ስሜት የምትሠራም አይደለችም፥ ይልቅስ ከእግዚአብሔር ጋር ባለን አንድነት የምትረዳ ልዩ ሀብት ናት። ጌታ ራሱ "እኔ መንገድ እውነትና ሕይወት ነኝ" እንዳለ፥ እርሱ ባሳየን የአርአያነት ተግባራዊ የኾነ የእርስ በእርስ ፍቅር መንገድነት፥ እውነት የኾነውን የእርሱን ቃል አክብረን፥ ወደ ሕይወት መግባት አለብን። መንገዱን ካላገኘን እውነትን ሕይወትንም ማግኘት አንችልም። ስለዚህ ከግብዝነት ለመውጣት ስለ እውነት በእውነት መኖር መጀመር አለብን። በእውነተኛ የሕይወት ጎዳና ውስጥ እውነተኛ ፍቅር እና እውነተኛ ጣዕም ያለው ሕይወት አለና። ቆም ብለን አኗኗራችንን እንመርምር፥ የገፋናትን እውነት እንመልሳት፥ የጠላናትን አንድነት እንፈልጋት፥ ይህን ጊዜ የምናመልከው አምላክ ከግብዝነት እሳት ያድነናል። ይህ እሳካልኾነ ግብዝነታችንና ተመጻድቋችን ለማናስበው ትልቅ ችግር ይዳርገናል። ማስመሰላችንም ሕይወታችንን መራራና ርባና ቢስ ያደርግብናል፥ የሕይወት ብርሃንም ይነሣብናል። ይህን ኹሌም በማስተዋል ወደየ ልቡናችን እንመለስ!

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

19 Sep, 11:26


የማልገባ ልኾን እችላለሁ ብለን አርቀን አይተን እናለቅሳለን። ራሳችንን ስናይ ከማንም በእርግጠኝነት የምናንስ መኾናችን ይረዳናል። ዘፈን የሚዘፍኑ፣ የሚያመነዝሩ፣ የሚሰርቁና መሰል ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ኹሉ ከእኛ የሚበልጡ እንደ ኾኑ ከልብ ይሰማናል። ፈያታዊ ዘየማን ከዚያ ኹሉ የሽፍትነት ሥራ በአንዴ ተላቆ የክርስቶስ የመስቀል ላይ ወዳጅ መኾኑን ኹሌም እናስተውላለንና!! ራስን በማየት መኖር ውስጥ ራስን ማካበድ፣ የተለየው ነኝ ብሎ ማሰብ፣ ራስን ማክበር፣ ራስን ከሌሎች ኹሉ ከፍ ከፍ አድርጎ መቍጠር፣ አይመጥነኝም፣ አትመጥነኝም እያሉ መዘማነን ኹሉ አይኖርም። ራሱን የሚያይ ሰው ኹሉን ንጹሕ አድርጎ ያያል። መጽሐፍ "ለንጹሕ ኹሉ ንጹሕ ነው" እንዲል። አመንዝራው፣ ሌባው፣ ጨካኙ፣ ሌላውም ኹሉ ከእርሱ የተሻሉ እንደ ኾኑ አድርጎ ይቈጥራልና።

++++++ ++++++++ ++++++++++

በቃ ዋናው መፍትሔ ራስን ማየት ነው። ራሳቸውን አይተው የወደቁ እነማን ናቸው? አጥርቶ በሚያይ በእግዚአብሔር ፊት ለፍርድ ከመቆማችን በፊት ኹል ጊዜ ራሳችን ራሳችንን እያየን በራሳችን ላይ እንፍረድ። እኔ ነኝ ዋናው ኃጢአተኛ ከልባችን እንበል። አባ ሙሴ ጸሊም ለታላቅ ክብር የበቁት ራሳን በማየት መሰላል ላይ ወጥተው ነው። በኃጢአተኛ ሰው ፍረድ ሲባሉ የራሳቸውን ኃጢአት ማሳያ በማዳበሪያ አፈር ተሸክመው፥ እርሱንም ቀድደው፥ ለራሳቸው ከልባቸው ይህ የእኔ ኃጢአት ነው፥ ማዳበሪያውን መልቶ ይፈሳል አሉ። እንግዲያውስ እንዴት በሌላው ይፍረዱ!! እርሳቸው ራሳቸውን አይተው ሌሎችንም ወደ ራሳቸው እንዲመለሱ አደረጓቸው። ማንኛውንም ችግር ለመፍታት ወደ ራሳችን መመለስ አለብን። ራስን በማየት ውስጥ ራስን ማወቅ አለ። ራስን በማወቅ ውስጥ በራስ ላይ መፍረድ አለ። በራስ መፍረድ ውስጥ ደግሞ ተአምኖተ ኃጢአት አለ። ኃጢአትን በማመን ውስጥ ደግሞ አንብዓ ንስሐ አለ። በአንብዓ ንስሐ ውስጥ የእውነት የኾነ ጸጸት አለ። በዚህ መንገድ ከኾነ ከዲያብሎስ ወጥመድ እንተርፋለን። ችግሩ፥ ራሳችንን ባለማየት ስለ ራሳችን የደነቆርን ኾነን ሳለ ሌላውን እናማለን፣ እንንቃለን፣ እንሰድባለን፣ እናንቋሽሻለን፣ እንጠላለን፣ በሌላው እንመቀኛለን፣ እንኲራራለን ... ብቻ ብዙ እናደርጋለን። ይህ በእውነቱ አሳዛኝ ደረጃ ላይ መድረሳችንን የሚያመለክት ነው። ስለዚህ ወደ ራሳችን እንድንመለስ አምላካችን ይርዳን አሜን!

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

19 Sep, 11:26


+++++++#ወደ_ራስ_ማየት#++++++++

ወደ ራስ መመልከት የራስን ኃጢአት ወደ ማሰብ ያመጣል። ወደ ራስ መመልከት በውስጥ የሚንቦገቦገውን የዝሙት እሳት ለማብረድ ያግዛል። ወደ ላይ ለመውጣት ራስን ከመመርመር እንጀምር። ብዙ ችግሮች ችግር ኾነው እየቀጠሉ ያሉት ወደ ራሳችን ማየት ስላቆምን ነው። እኛ የሚመስለን እኛነታችንና እየኾን ያለው እኛነታችን ይለያያል። ወዳጆች ሆይ ወደ መልካም መንገድ መግባት ትፈልጋላችሁን? እንግዲያውስ ውስጣችሁን መርምሩ። ለራስህ ራስህን ሐኪም አድርገህ መርምር። ያልኾንከውን የኾንክ አይመስልህምን? ጥሩ ሰው እንደ ኾንክስ አይሰማህምን? ይህ ኹሉ ምንጩ ወደ ራስ ማየት ማቆምህ መኾኑን አስተውል! ራሱን የማያይ ሰው አዎንታዊነት አይኖረውም፤ በሰዎች ላይ ያየውን ነገር ቶሎ ብሎ ሌላ ትርጒም እየሰጠ በውስጡ ይሰቃያል፤ ወይም ከሌላው ይልቅ ራሱን የተሻለ እንደ ኾነ አድርጎ ያስባል።

ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ "ካህናትን በሚገባ አክብር። ለመዓርጋቸውም ክብር ስጥ፤ ሥራቸውን አትመርምር። በመዓርጉ ካህን መልአክ ነውና። በሥራው ግን ሰው ነው። በእግዚአብሔር ቸርነት ቄሱ በሰው ልጆችና በእግዚአብሔር መካከል ያለ አማላጅ ነው። የሰዎችን ስሕተት አትፈልግ። የወዳጅህን ኃጢአት አትግለጥ። የጎረቤትህን መጥፎ ጎን በንግግርህ አውጥተህ አትድገመው። በፍጥረት ላይ ፈራጅ አልኾንክምና። በምድር ላይ ገዥ አይደለህምና። ጽድቅን ካፈቀርክ ራስህን ገሥጽ። ለራስህ ኃጢአቶች ፈራጅ ለመተላለፍህ ብቻ ተነሳሒ ኹን። የሰዎችን መጥፎ ምግባር በተንኮል አትመርምር። ... በወዳጅህ ላይ ከተቆጣህ በእግዚአብሔር ላይ መቆጣትህ ነው። በልብህ ቍጣን ከተሸከምክ በጌታ ላይ መነሣትህ ነው። ድፍረትህም ከፍ ይላል። በክፉ ቅናት ከገሠጽክም ግሣጼው ኹሉ የክፋት ነው። በጎነት በውስጥ ከኖረ ምንም ጠላት በምድር ላይ አይኖርህም። እውነተኛ የሰላም ልጅ ከኾንክ በማንም ሰው ላይ ቍጣን አትቆሰቁስም። መቆጣትን የምታፈቅር ከኾነ በክፉው ነገር ተቆጣ ከዚያን ያንተ ኾኖ ታገኘዋለህ። የምትፈልገው ጦርነትን ለማወጅ ከኾነ ሰይጣን አማካሪ ኾኗል። ለመቆጣት ብትመኝ በአጋንንት ላይ ተቆጣ። በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረውን ሰው የምትሳደብ ከኾነ የነፍሰ ገዳይ ቅጣት ይገባሃል። ሰውን ሙልጭ አድርጎ መሳደብ የእግዚአብሔርን አርአያ መሳደብ ነው" እንዲል። (Nicene and post Nicene Fathers second series V 13)።

++++++ ++++++++ ++++++++++

ለሀገራችን ጥፋትና ክፉ ሴራ ኹሉ መነሻው እኔ ነኝ፣ እኔ ስለ በደልኩና ከበደሌም መመለስ ስላልፈለግሁ ነው እንበል። ክርስቶስን ሩቅ ቦታ አንፈልገው እርሱ እዚሁ አጠገባችን ነው። በእርግጥም ራሳችንን ማየት ስንጀምር ድፍረታችን የት እንደ ደረሰ ይገባናል። በልምድ ደጋግመን እየፈጸምን ያለው ኃጢአት ኹሉ ተነቅሎ የሚወድቀው ራሳችንን ስናይ ነው። እልህኝነታችን ዋና ምንጩ ራሳችንን ማየት ማቆማችን ነው። በብዙ ደባ የተተበተብነው ከወደቅንበት የአስተሳሰቅ ውድቀት የተነሣ ነው። የአስተሳሰብ ውድቃታችን ዛሬም እንደ ትናንቱ ለምን የኾነ ይመስላችኋል? ራሳችንን ከጥልቅ ልቡናችን ስለማናይና ወደ ስንፍና ሕይወት ገብተን ከሚገጥመን ዝንጋዔ የተነሣ ነዋ! መልካም የኾነውን ወዲያው እንረሳለን፥ ምክንያቱም ራሳችንን አናይማ! የጉዳታችን ዋና ምንጭ ራስን አለማየት ነው።

++++ ++++ ++++++++ ++++++++

ማርያም ኃጥእት ለጽድቅ የበቃችው ራሷን ከማየት ጀምራ ነው። ራስን ማየት ወደ ንስሓ የሚያስገሰግስ ታላቅ መንገድ ነው። ማርያም ግብጻዊት በመስታወት ፊት ቆማ ውጫዊ መልኳን ታይ የነበረችው ወዲያው ወደ ራሷ ውስጣዊ ማንነት መለስ ብላ ስትመረምር እጅግ አስጠላታም ኾና አገኘችው። ራሷን ራሷ ጠላችው። የኃጢአቷ ክምር የነፍሷን መልክ አክስሎታልና። ስለዚህ ከዓይኖቿ የማይቋረጡ እንባዎች እንደ ምንጭ ይፈልቁ ጀመር። እንግዲህ የዚህ መነሻው ራስን ማየት ነው። ራስን ማየት ቅዱስ ጴጥሮስን ንስሓ እንዲገባው እንዳደረገው አስተውል። ታላቅ ሐዋርያ የኾነ እርሱ ራሱን ማየት ባቆመ ጊዜ አምላኩን አላውቀውም ብሎ ክዶት ነበርና። ወደ ራሱ ሲመለስ ግን የፈጸመውን በደል ተረድቶ የንስሐ እንባን አፈሰሰ። ምናልባት በሕይወታችን ውስጥ ክርስቶስን አላውቀውም ብለን ይኾን? በሕይወታችን ውስጥ የክርስቶስን ፈቃድ የማንፈጽምና የየግል ስሜታችንን ለማርካት ብቻ የምንኖር ከኾነ፡ በእርግጥም ክደነዋል ማለት ነው! ከሚመጣብን መከራ ለመትረፍ ብለን የዘለዓለማዊ ሕይወት ምንጭ የኾነውን ረስተን እየተቀመጣጠልና እያሽካካን የምንኖር ከኾነ ውጤቱ መራራ ነው የሚኾንብን! እንግዲህ ትክክል ያልኾነን ነገር መርጠን ትክክል የኾነውን ትተን የምንኖር ልብ እንበል! ምርጫችን የዘመናት ኀዘን ምክንያት ሊኾነን ይችላልና። ስለዚህ ወደ ራሳችን እያየን በፈሪሐ እግዚአብሔር ኾኖ ለመኖር እንወስን።

+++++ +++++++ +++++++++++++

ብዙ ማውራት ስለምንወድ ስለ ራሳችን ድክመት ማየት አቃተን። ከምንነቅፈው ሰው የበለጠ የሚያስነቅፍ ነገር እንዳለብን አልገባ ያለን ራሳችንን ሰለማናይ ነው። የቅዱሳን ሕይወት መነሻውም መድረሻው ራስን በማየት ላይ የተመሠረተ ነው። ራስን ማየት ራስን ወደ መናቅ፣ ራስን መናቅ ራስን ወደ መካድ፣ ራስን መካድ የክርስቶስን መስቀል ወደ መሸከም ልዕልና ያደርሰናል። የትሕትና ዋናው መግቢያው ራስን ማየት ነው። ጌታችን ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወልዶ ያደረጋቸው የአርአያነት ሥራዎች በሙሉ እኛን ለማንሣትና ራሳችንን እንድንመረምር ለማድረግ መኾኑን ልብ እንበል። ሰማዕታት ዓለምን ንቀው ደማቸው እስኪፈስ መታገሣቸው እኛን ለማገዝና ራሳችንን እንድናይ ለማስቻል ነው። መነኮሳት ስለ ክርስቶስ የሚመነኩሱት እኛ ቢያንስ ሥርዓት ይዘን የእነርሱን ታላቅነት በእኛ ታናሽነት አንጻር እንድናይ ለማበርታት ነው። ብርቱዎቹን ስናይ ወደ መቍረጥ እንወጣለን፤ ወይኔ! እኔ ደካማው ዓለም ላይ ተጣብቄ ያማረ የጣመ የምበላ ብለን በክርሰቶስ ፍቅር እንድንቃጠል መስታወት ኾነው ሊያሳዩን ነው። እኔ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ብዬ ትንሽዬ ነገር መተው ሲያቅተኝ ከኔ ወገን ያሉ ግን ኹሉን ትተው ተከተሉት፣ እኔ ልብሴ አላማረም ብዬ ስጨነቅ እውነተኞቹ መናኞች ግን ልብሳችን ክርስቶስ ነው ብለው ማረፊያቸው እርሱን አደረጉ። እንዲህ እያልን በጥልቀትና በተመስጦ ስንመረምር ምን ያህል የእውነት ሩቅ መኾናችንን መረዳት እንችላለን። ከዚያን ኹሌም ራሳችንን ያነስን እንደ ኾን ቈጥረን መኖር እንጀምራለን።

++++++ +++++++ ++++++++++++

ጌታችን ዝቅ ብሎ የሐዋርያትን እግር ሲያጥብ ይሁዳ ራሱን ማየት የማይፈልግ በመኾኑ ምክንያት ዝም ብሎ ታጠበ። ጌታ ዝቅ ያለው በይሁዳ ልብ ውስጥ ያለው የገንዘብን ፍቅር ዝቅ ለማድረግ ነበር፤ ይሁዳ ግን ግትር በመኾኑ ምክንያት በፈቃዱ ከሕይወት መንገድ ወጣ። በጌታችን እጅ የታጠቡ የይሁዳ እግሮች ወደ ጽድቅ ከመገሥገሥ ይልቅ በተቃራኒው የሚገሠግሡ ኾኑ። ጌታችን የይሁዳን እግር ሲያጥብ ይሁዳ የራሱን ልብ በፈቃዱ ስለ ዘጋው ሳይታጠብ ቀረ። ጌታችን ልቡናችንን የሚያጥብልን በእኛ ፈቃድ ላይ ተመሥርቶ ስለ ኾነ የይሁዳን ደንዳናነት ተረድቶ ዝም አለው። የምንቀባጥረው፣ ራሳችንን የምናዘማንነው በእርግጥም ራሳችንን ስለማናይ ነው። ራሳችንን ማየት ስንጀምር ባዶ መኾናችን ይገባናል። ኃጢአት የሚሠሩ ሰዎችን ስናይ ይህ ሰው ንስሓ ገብቶ ይመለሳል እኔ ግን ነገ ኃጢአት ሠርቼ ንስሓ

ዮሐንስ ጌታቸው

16 Sep, 10:26


) ይህ ጎርጎርዮስ የተባለ ሊቅ የሰናፍንጭን ቅንጣት በኢየሱስ ክርስቶስ መስሎ አስተምሯል። በአትክልት ስፍራ በመቀበሩ የሰናፍንጭ ቅንጣት ነው፤ በመነሣቱ ዛፍ ነው። በመሞቱ የሰናፍንጭ ቅንጣት ነው፤ ሞትን ድል አድርጎ በመነሣቱ የሰናፍንጭ ዛፍ ነው። በሥጋው ብቻ የሰናፍንጭ ዘር ነው፤ በግርማዊ ኃይሉ ግን የሰናፍንጭ ዛፍ ነው። በእኛ በመታየቱ የሰናፍንጭ ቅንጣት ነው፤ ነገር ግን ከሰው ልጆች ሁሉ ያማረ በመኾኑ የሰናፍንጭ ዛፍ ነው። የዚህ ዛፍ ቅርንጫፎች የተቀደሱ ስብከቶች ናቸው። ... በዚህ ዛፍ ላይ ባሉ ቅርጫፎች ላይ ርግቦች ያርፉበታል። ርግብ የተባሉት የንጹሐን ነፍሶች ናቸው፤ ከዚህ ምድር ሐሳብ ተለይተው በበጎ ምግባራት ክንፍ ከዚህ ዓለም ተጋድሎ በኋላ ወደላይ ይወጣሉ።" በማለት እጅግ ድንቅ ምሥጢር አስቀምጦልናል። የሰናፍንጭ ቅንጣት በተባለው የጌታችን ሞት አመካኝነት በኋላ ላይ የሰናፍንጭ ዛፍ የተባለውን ትንሣኤውን እንረዳለን። አይሁድ ክርስቶስ እንዲገደል ሲያደርጉ የሚነሣ አልመሠላቸውም፤ ምክንያቱም እንደ ሰናፍንጭ ቅንጣት ትንሽና ቀላል አድርገው አስበውታልና ነገር ግን እነርሱ ከናቁት ሞት ዛፍ የተባለው ትንሣኤ ይበቅላልና።

ይህም ብቻ ሳይኾን የክርስቶስ ሞቱና ትንሣኤው የእኛንም ሞትና ትንሣኤ አመልካች ነው። አባታችን አዳም ከነበረው ታላቅ ክብር ዕፀ በለስን በልቶ እንደ ሰናፍንጭ ቅንጣት ከፍጥረት ኹሉ አንሦ ሞትን ገንዘብ አደረገ። ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ አዳምን ያሳተው ለዘለዓለም ከእግዚአብሔር ለይቶ ለማስቀረት ነበር። የኾነው ኾኖ አምላካችን ክርስቶስ ግን በመርገመ ሥጋና ነፍስ ጎስቁሎ በርደተ መቃብር ላይ ርደተ ሲዖልን ገንዘብ አድርጎ የሚሰቃየውን አዳምን ያለበት መቃብር ድረስ ገብቶ እንደ ሰናፍንጭ ዛፍ ክብሩን በዓለም ትልቅ አደረገው። ሰናፍንጭ ክርስቶስን የሚክል ሲኾን ውጩ ቀይ መኾኑ መለኮትን የሚያሳይ ነው፤ ውስጡ ነጭ መኾኑ መለኮት የተዋሐዳት ሥጋ ፀአዳ ወይም ምንም ዓይነት የኃጢአት ትንታ የሌለበት ንጹሕ መኾኑን የሚያመለክት ነው። በሌላ በኩል ደግሞ ቀዩ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሲል የተቀበለውን የደም መከራ የሚያሳይ ሲኾን፤ ነጭ መኾኑ በእርሱ መከራ እኛ የምናገኘውን ክብር የሚያመላክት ነው። እንግዲህ በአጭሩ ሰናፍንጭን ስናስብ እነዚህን መልእክታት ማሰብ ብንችል መልካም ነው።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

16 Sep, 10:26


++++++##የሰናፍንጭ_ቅንጣት##++++++

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።


የሰናፍንጭ ነገር በወንጌል በተደጋጋሚ ተነግሯል። ማር 4፥31፣ ማቴ 13፥31፣ ሉቃ 13፥18። በአጭሩ ከሰናፍንጭ ቅንጣት የምንማረውን መልእክት እናያለን። ይህ የሰናፍንጭ ቅንጣት ጉዳይ በብዙ ሊቃውንት ዘንድ ትኩረት ያገኘ ጉዳይ ነው። እግዚአብሔር ለእኛ ስለሚራራልን እኛን ለማገዝ በብዙ ኅብረ አምሳል የገዘፈውን የሃይማኖት ምሥጢር ራሱ አምላካችን የሰውን ሥጋና ነፍስ ነሥቶ በተወለደ ጊዜ አስተምሮናል። ጴጥሮስ ክርስቶሎጎስ የተባለው ሊቅ የሰናፍንጭ ቅንጣትን አስመልክቶ ያስተማረውን ቀንጨብጨብ አድርገን እንመልከተው። የሰናፍንጭ ዘር ከኹሉም ወደሚልቅ ቁጥቋጦ ያድጋል። ... የሰናፍንጭ ቅንጣት የአማኞች ተስፋ ድምር ነውን? ... ይህቺ ከኹሉ የምታንሰው የእግዚአብሔር ፍጥረት ከጠቅላላው ሰፊ ዓለም ትበልጣለች። ... በእርግጥ የሰናፍንጭ ዘር የእግዚአብሔር መንግሥት ምሳሌ ናት። ... ልክ እንደ ሰናፍንጭ ቅንጣት በድንግል ማኅፀን ገነት ውስት ተተከለ፤ ወደ መስቀል ዛፍም አደገ፤ የዚህም ዛፍ ቅርንጫፉ በዓለም ኹሉ ይዘረጋል። ... ክርስቶስ ንጉሥ ነው፤ ምክንያቱም የሥልጣናት ኹሉ ምንጭ ነውና። ክርስቶስ መንግሥት ነው፤ የንግሥና ክብር በሙሉ በእርሱ ዘንድ ነውና። ... ክርስቶስ የሰናፍንጭ ዘር ነው፤ ምክንያቱም የመለኮትን አለመወሰን ከትንሽየው ሥጋና ደም ጋር አስማምቷልና። ከዚህ ተጨማሪ ምሳሌ ትሻላችሁን? ክርስቶስ ኹላችንንም በእርሱ ለማደስ ኹሉንም ኾኗል። " እያለ ያመሰጥራል። (Commentary by Peter Chrysologus Sermon 98: PL 52, 474-76) ።

በዚህ የሊቁ ትምህርት ውስጥ ብዙ ቁም ነገሮችን መማር እንችላለን። ከዚህ የሰናፍንጭ ቅንጣት ዕድገትን እንማራለን። አንድ ክርስቲያን ኹል ጊዜ በእምነቱም ኾነ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ማደግ አለበት። ከማይታየው እምነት እስከሚታየው እምነት ከፍ ማለት አለበት። ከተራ ምእመንነት እስከ ደም ሰማእትነት ከፍ ማለት ያስፈልጋል። በኃጢአት ምክንያት እንደሰናፍንጭ ቅንጣት ያነሰው በጎነታችንን በንስሓና በተጋድሎ በማሳደግ መትጋት እንዳለብን መማር እንችላለን። ይህም ብቻ ሳይኾን የክርስቲያኖችን በአንድነት የመጸለይና የመትጋት ተስፋ ማየት እንችላለን። በአንድነት ስንጸልይ፣ ስንጾም ተስፋችን ከሰናፍንጭ ቅንጣትነት ወደ ዛፍነት ያድጋል። ስለዚህ ተስፋን ማጣት ድል እንዳያደርገን በአንድነት መትጋትና እግዚአብሔርን መለመን አለብን። ከዚህ ኹሉ በላይ በዚህች የሰናፍንጭ ቅንጣት የክርስቶስን በቅድስት ድንግል ማርያም ማኅፀን መፀነስ እንማራለን። ሰማያዊው ንጉሥ እንደ ሰናፍንጭ ቅንጣት በድንግል ማሕፀን መፀነሱ እንደ ምን ይደንቅ ይኾን! የእርሱ ፅንሰት በማሕፀን እየተቆራኘ ፅንሶችን የሚያስጨንቀውን ሰይጣንን ቀጥቅጦ ለማጥፋት ነው።

የሰናፍንጭ ቅንጣት ትንሽ እንደ ኾነ የጌታን ከድንግል የመወለድ ነገር አምላክነቱን የሚክዱ አይሁድ አሣንሰው በማየት የፍጡር ልጅ ፍጡር አሉት። ይህቺ የሰናፍንጭ ቅንጣት የተባለችው የጌታን ፅንሰት የምታመለክት ቅንጣት ወደ ሰናፍንጭ ዛፍነት (ወደ መስቀለ ክርስቶስ) በማደግ ዓለምን በሙሉ ተሸከመች። የሰናፍንጭ ዛፍ የቅዱስ መስቀል ምሳሌ ነው። መስቀል ዓለምን ለማዳን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገባበት መቅደስ ስለ ኾነች ሽፍታው ጥጦስ በቀኝ በኩል የተሰቀለው ወንበዴ በላዩአ ላይ ዐረፈባት። የክርስቶስ የማዳን ነገር ከፅንሰት የሰናፍንጭ ቅንጣትነት ተነሥቶ ወደ መስቀል የሞት ካሣነት አደገ። ብዙ ተጠራጣሪዎችም በዚህ የመስቀል ዛፍ አማካኝነት ወደ እውነት መንገድ እንደ ወፍ እየበረሩ መጥተው ዐረፉበት። ከሰናፍንጭ ቅንጣትነት ወደ ዛፍነት ማደግ ማለት የሰናፍንጭ ቅንጣት የተባለው ሰውነት በተዋሕዶ ምሥጢር ከአካላዊ ቃል ጋር አንድ በመኾን በሰናፍንጭ ዛፍነት መገለጥ ነው። በሌላ አገላለጽ ትንሿ የሰውነት አካልና ባሕርይ በተዋሕዶ አማካኝነት ትልቁን የመለኮትን ባሕርይና አካል ገንዘብ በማድረግ እጅግ መክበሯን መናገር ነው። ትስብእት የሰናፍንጭ ቅንጣት ናት፤ መለኮት የሰናፍንጭ ዛፍ ነው። የኹለቱ ተዋሕዶ ማለት የሰናፍንጭ ቅንጣት ቅንጣት መኾኗ እንዳለ ኾኖ ዛፍነትን ታስገኛለች። የሰናፍንጭን ዛፍ ቅንጣት ነው ማለት አይቻልም፤ ቅንጣቱም የለም ዛፉ ብቻ ነው ማለትም አይቻልም። አምላካችን እግዚአብሔር በቅንጣት የተመሰለውን የእኛን አካልና ባሕርይ በተዋሕዶ ከእርሱ የማይወሰን ማንነት ጋር አስማማው! ይህ በእውነቱ እጅግ አስደናቂ ምሥጢር ነው።
__ ___
ይህቺ የሰናፍንጭ ቅንጣት ሌላም ምሥጢር አላት፤ (commentary from the Navarre Bible) "ተካዩ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ የሚተክልበት ቦታ ዓለም ነው። የሰናፍንጭ ዘር የወንጌል ስብከትና የቤተክርስቲያን ምሳሌ ነው።" በማለት የሚያብራሩ አሉ። ከትንሽ የሰናፍንጭ ቅንጣትነት ወንጌልና ቅድስት ቤተክርስቲያን በዓለም ኹሉ ትሰፋለች። ዓለም በሙሉ የእውነትን ወንጌል ይሰበካል፤ የቅድስት ቤተክርስቲያንንም ክብር ያውቃል። በብዙዎች ዘንድ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንደ ሰናፍንጭ ቅንጣት ትንሽ ተደርጋ ቦታ ሳይሰጣት ትኖር ይኾናል፤ የኋላ ኋላ ግን በዓለም ኹሉ ስትሰፋና ስትነገር፥ ዘሪዋ ኢየሱስ ክርስቶስም ኃይል ተአምራቱን ሲያደርግ አይተው ብዙ ሰዎች ወደ መዳን ይመጣሉ።
___ ___
የሰናፍንጭ ቅንጣትን ሊቁ አውግስጢኖስ ከክርስቲያን ሕይወት ጋር አገናኝቶ አስምሯል። (St. Augustine says, in the work already cited [Serm. 33 de Sanc. ])። የሰናፍንጭ ቅንጣት አንደኛ በእምነት የተመሉ ሰዎችን የሚያመለክት ነው፤ ለምሳሌ ቅዱሳን ሐዋርያትን የሚያሳይ ነው፤ ወይም መከራ የሚቀበሉ ክርስቲያኖችን ወይም ሰማዕታትን የሚያመለክት ነው በማለት ያስረዳል። በእርግጥም ሰማዕታት ስለ ክርስቶስ ፍቅር ሲሉ እንደ ሰናፍንጭ ቅንጣት የሚደቆሱና በእነርሱ መደቆስ ማለትም መታረድ፣ መገረፍ፣ መቃጠልና መሰቀል አጋንንታዊ ሐሳብ ያላቸውን አላውያን ነገሥታት ድል ያደርጋሉ። ሰናፍንጭ ውጯ ቀይ ውስጧ ግን ነጭ ነው። ሰማዕትነት ውጪው ቀይ ነው፤ ይህም ማለት ደምን እስከማፍሰስ ድረስ መከራና ሥቃይ የሚቀበሉበት ሕይወት ነው። ውስጡ ነጭ መኾኑ በሰማዕትነት ሕይወት የሚገኘው ክብር ምንም ዓይነት ጥቍረት የሌለበት እንደ በረዶ ነጭ ነው። በሌላ በኩል ውጩን ስናየው ጭንቅ በመኾኑ ምክንያት የመከራንና የሥቃይን ሕይወት እንዳንፈራና እንዳንሰቀቀ ውስጡን ነጭ በማድረግ ተስፋችን የለመለመ መኾኑን ያስገነዝበናል። ይህም ብቻ አይደለም በታላቁ ጸሎታችን ኹል ጊዜ "ወደ ፈተና አታግባኝ" በማለት የምንጸልየው፥ ሰማዕትነትን አታምጣብኝ ለማለት ሳይኾን በሚደርስብኝ መከራ በመሰቀቅ ወደ ክሕደት እንዳልገባ አድርገኝ ለማለት ነው።
___ ___
St. Gregory ( lib. 19 Moral. c. 11.

ዮሐንስ ጌታቸው

12 Sep, 11:53


የቅዱስ ዮሐንስ ምግቡ አንበጣ (Locust) ነው። አንበጣ የከንቱ ድካም ምሳሌ ነው። በሌላ በኩል ከአንበጣ መንጋ የሚሰማው ድምፅ እጅግ አስጠሊታም ነው። ስለዚህ አንበጣ መብላት ዋናው ምሥጢር በሚያስጠላና በሚከረፋ የኃጢአት ሥራ ውስጥ የሚኖሩትን ሰዎች በፍቅር ስቦ በደግነት አቅርቦ የሚጣፍጥ ምግብ አድርጎ መብላትን ነው። የማይበላ ሥራ ይሠሩ የነበሩ ኃጥአን በቅዱስ ዮሐንስ ስብከት በኩል የሚበላ ወደ መኾን መምጣታቸውን የሚያመልክት ነው። በሌላ በኩል የአሕዛብ ቤተክርስቲያን በክርስቶስ አምላክነት አምና በነቢያት አፍ እስክትሰበክ ድረስ ከበረች ማለት ነው። አዲስ ዓመት የሚከበረው ይህን በማድረግ ነው።

አንበጣ ከምድር ከፍ ብሎ በሰማይ ነው የሚበረው! ይህ መንፈሳዊ ተመስጦ ነው። ዮሐንስ የበላው ይህን የተመስጦ ምግብ ነው። ወደ ጥልቅ መንፈሳዊ ተመስጦ ውስጥ ገብቶ ምግቡን መልአካዊ ምስጋና አደረገው። እግዚአብሔርን ከጥልቅ ልቡ ውስጥ ሥሎት በተሰጠው የተመስጦ ጸጋ ክንፍ በሐሳቡ ወደ ሰማይ በረረ! አዲስ ዓመት የሐሳብ ወደ ሰማይ መብረሪያ እንጂ በምድር ላይ በሐሳብ ደረትነት እንደ መሳብ መንወዛወዝ አይደለም።

=====+++++=====+++======

ሶፍሮንየስ (Sophronius) የተባለ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስን “የሰውን ሥጋ የለበሰ መልአክ" ይለዋል። ይኸው ልቅ ቅዱስ ዮሐንስ ወደ ምድረ በዳ የገባው የመላእክትን ኑሮ ለመኖር ነው ይላል። ይህ መንገድ ደግሞ ሰው ያለ መጠለያ ሊኖር የሚችል መኾኑን አመልካች ነው። አኹን እኛ የሠራነውን ዓይነት ቤት ሳይሠሩ በምድረ በዳ የሚኖሩ ቅዱሳን መኖራቸው መጠለያን እንደ ሕይወት ዋናና መሠረታዊ ዓላማ አድርገን ሐሳባችንን በምድራዊ መጠለያ እንዳንቀብረው ለማስገንዘብ ነው። አዲሱን ዓመት አዲስ የሚያደርገው የምንኖረው አኗኗር ነው። የዮሐንስን ዓመት በዮሐንሳዊ ሥራ ካላከበርነው እኛ ያለንበት ዐውደ ዓመት ሌላ ዐውደ ዓመት እንጂ የዮሐንስ አይደለም። ስለዚህ የእኛ ዓመት ዐውደ ዓመት የሚኾንልን የዮሐንስን ሥራ ለመሥራት ከጥልቅ ውስጣችን ስንሻ መኾኑን ተረድተን ዓመታችንን እውነተኛ እናድርገው።

መልካም ርእሰ ዓውደ ዓመት ቅዱስ ዮሐንስ ይኹንልን።

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

12 Sep, 11:53


###ርእሰ_ዐውደ_ዓመት_ዮሐንስ###

=======+++++=+========+=
አዲስ ዓመት የሚጀምረው ከቅዱስ ዮሐንስ የሰማዕትነት ዕለት ስለ ኾነ ከዓመቱ ጋር አብሮ አጥማቄ “ሥግው ቃል" ቅዱስ ዮሐንስ ይታሰብበታል። ቅዱስ ዮሐንስ የልደቱ ዕለት በደስታ ተጀምሮ በዕረፍቱም ዕለት በደስታ ይከበራል። በበረከት ጀምሮ በበረከት ተጋድሎውን ጨረሰ። የሰማዕታት የሰማዕትነት ዕለት ለዘለዓለማዊ ሕይወት የሚወለዱበት ዕለት ስለ ኾነ “የልደት ዕለት" ተብሎ በቅድስት ቤተክርስቲያን ይከበራል።

=====++=+=+=+=========++
ቅዱስ ዮሐንስ ብዙ ልዩ ነገሮች ያሉት ልዩ የእግዚአብሔር አገልጋይ ነው። እስኪ ከስሙ እንጀምር “ዮሐንስ" ማለት የእግዚአብሔር መንግሥት (The Kingdom Of God) ማለት ነው። ይህ የስሙ ትርጒም “የእግዚአብሔር መንግሥት ቀርባለችና ንስሓ ግቡ" የሚለውን ስብከቱን ያመለክታል። ለቅዱስ ዮሐንስ “ስሙ ስብከቱ! ስብከቱ ስሙ ነው።" በዚህ ዘመን እንዳለን ሰዎች ስሙን ተሸክሞት ብቻ ያለ ሳይኾን በተግባር እየኖረው የሚሰብከው ልዩ አገልጋይ ነው። አዲስ ዓመት አዲስ የሚኾነው ንስሓን በመጠማትና ከልብ በመሻት ስንጀምረው ወይም የመንግሥተ ሰማያትን ሥራ ብቻ ለመሥራት አቅደው ሲጀምሩ ነው።

==========+=====+++=====

ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ደግ ነው (God is Gracious) ማለት ነው። ይህ ደግነት ከቂምና ከበቀል የራቀ በፍጹም ቸርነት ላይ የተመሠረተ ነው። በአዲስ ዓመት ውስጥ ገብቶ መኖር ማለት በደግነትና በርኅራኄ ውስጥ ገብቶ መኖር ማለት ነው። ለተራበ፣ ለተጠማ፣ ለታረዘ፣ ለታመመ የሚራራ ደግነትን የሚሠራ እርሱ በእርግጥም በአዲስ ዓመት ውስጥ ገብቷል። ይህ ደግነት ማስመሰልና መገበዝ የሌለበት ስለ ኾነ “ለራስ ራስን ደግ በማድረግ ይጀምራል።" ለራስ ደግ መኾን ማለት በንስሓ በር ራስን ወደ ደግነት ቤት (ወደ ምሥጢረ ቁርባን) ማቅረብ ነው።

====++++====++===++++===

የቅዱስ ዮሐንስ የስሙ ትርጒም የእግዚአብሔር ጸጋ (The Grace of God) ማለት ስለ ኾነ የማያልቅ ነው። ጸጋ እግዚአብሔር ተሰፍሮና ተለክቶ የማያልቅ እንደ ኾነ የቅዱስ ዮሐንስም የተጋድሎና የቅድስና ሕይወት ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለም። በዚህ ዓለም ኃጢአት ውስጣችን የቆሸሸብንና ከጸጋ እግዚአብሔር የራቅን ሰዎች ወደ አዲሱ ዓመት የገባን አይምሰለን፤ አሮጌውን ይዘን አልለቅ ያልን አሳዛኞች እንጂ። ስለዚህ የርእሰ ዐውደ ዓመት ዮሐንስ ስሙ እንኳን ሕሊናችንን ወደ እግዚአብሔር የሚመራ ነው። በኹሉም መስመር ጸያሔ ፍኖት ነው።

===+++===+++=====++===+=

ርእሰ ዓውደ ዓመት ዮሐንስ ሳይንስ በጣም ለሰው ሕይወት መሠረት ናቸው ያላቸውን ሦስት ነገሮች ምግብ፣ ልብስና መጠለያን የገለበጠና የሕይወት ዋናው መሠረት እግዚአብሔር መኾኑን የመሰከረ ነው። የሳይንቲስቶች ዓላማ ሰውን ከእግዚአብሔር መለየት ነው። የሕይወትን ዓላማ መሥመር መበጠስና በስስ ክር ያያያዘ አስመስሎ ማጥፋት ነው። የሕይወት ዋና ዓለማው እግዚአብሔርን ማግኘት ነው። እርሱን ስናገኝ ሌሎች ኹሉ ይጨመራሉና! እርሱን ከሕይወታችን መዝገብ አስወጥተን በዚህ ዓለም ላይ ብቻ ኑሮን ከመሠረትን የሕይወትን ዓላማ ረሳነው ማለት ነው።

መጽሐፍ "መንግሥቱንና ጽድቁን ፈልጉ ሌላው ይጨመርላችኋል።" ያለን ሕይወታችን መመሥረት ያለበት በዚህ ጽኑዕ መሠረት ላይ ስለ ኾነ ነው። ቅዱስ ዮሐንስ ለዚህም መንገድ ጠራጊያችን ነው። ሳይንስ የሰውን ልጅ የመኖር ዓላማ መሬታዊ ብቻ አደረገው። የምትኖረው ለምግብ፣ ለመጠለያና ለልብስ ብቻ ነው በማለት ለዚህ ብቻ እንድንተጋና እንድንደክም አደረገን። በዘዴያዊ መንገድ ከኦርቶዶክሳዊው የመኖር ዓላማ ገፍትሮ በአሸዋ አስተሳሰብ ላይ ተከለን። ስኬትም እነዚህን ነገሮች ማግኘት ነው ብሎ ክርስቶስንና የእርሱ የኾኑ ቅዱሳንን አሳጣን። በዚህ አስተሳሰብ ከልጅነት ጀምሮ በእጅጉ አሰከረን። ስለዚህ ሰዎች እግዚአብሔርን ከመፈለግ ይልቅ እነዚህን ነገሮች ብቻ በጣም አትኩረው የሚፈልጉ ኾኑ። እንግዲህ አዲሱ ዓመት አዲስ ነው የሚባለው ይህን አስተሳሰብ ገልብጠን ክርስቶስን በማግኘት ጽኑዕ መሠረት ላይ ስንሠራው ነው። ጸያሔ ፍኖት ዮሐንስን አርአያ እናድርገው!! ከኋላው እንከተል። እንደ ዮሐንስ እግዚአብሔርን የሕይወታችን መሠረት ስናደርገው፡ እኛ ያስፈልጉናል የምንላቸውን ኹሉ እርሱ በቸርነቱ ይሰጠናል። እግዚአብሔር ኹሉን ማድረግ የሚችል ስለ ኾነ፥ እኛ ያስፈልጉናል በምንለውም በማንለው ሊያኖረን የሚችል መኾኑን ልብ እንበል። እንግዲህ ቅዱስ ዮሐንስ ወደ እግዚአብሔር ሐሳባችን የሚወስድል፥ በሰማይም ሕሊናችንን የሚተክል በጎ መንገድ መሪ ነው።

====+++====++++====+++====++

የዮሐንስ ልብሱ የግመል ጠጉር መኾኑን ስትሰሙ ምን ይታወሳችሁ ይኾን? “ባለ ጸጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፈሰ ይቀልላል" የሚለው አይታወሳችሁምን? ግመል የቤተ አሕዛብ ምሳሌ ነው፤ የመርፌ ቀዳዳ የርቱዕ ሃይማኖት ምሳሌ ነው። ስለዚህ የግመል ፀጒር መልበስ ማለት አሕዛብን በክርስቶስ አምላክነት አሳምኖ ወዳጅ ማድረግ ነው። አዲሱን ዓመት በመጠራጠር ሜዳ ላይ ሰይጣን የክሕደትን ኳስ የሚያስመታቸውን ወገኖቻችንን ወደ መዳን የምናመጣበት ሊኾን ይገባዋል። የግመል ፀጒር መልበሱ የኦሪት መጨረሻ የሐዲስ መግቢያ ላይ መነሣቱን የሚጠቁም መኾኑን ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አመልክቷል። አዲሱ ዓመት በዚህ መሠረት ላይ መሠራት አለበት። ኦሪታዊ ሥራ አኹን የተሻረ ነው። ይኸውም መሥዋዕተ ኦሪትና ግዝረተ ኦሪት ቀርቷልና። በዚሁ አንጻር ለእኛ አኹን ኦሪታዊ ሥራ የሚኾነው ለድኅነት የማያበቃ ሥራ በአጠቃላይ ነው። ይህ ከሕይወታችን ተነቅሎ ወንጌል ክርስቶስ መምጣት አለበት። የድኅነትን ሥራ ወይም የእምነት ሥራ የሚባሉትን በጎ ምግባራትን መሥራት አለብን። አዲስ ዓመት በዚህ ነውና አዲስ የሚኾነው!!

====++++========+++++===

የግመል ፀጒር ደመ ነፍስ ስለ ሌለው የግመልን ፀጒር መልበስ ማለት ከዓለማዊ ሥራ መለየት፤ በፍጹም መንፈሳዊነት መኖር ማለት ነው። ጌጣችን የዚህ ዓለም ኃላፊ ነገር አይደለም። የግመል ፀጒር መልበስ ማለት ለውጫዊ ልብስ በመጨነቅ አለመኖር! የቅምጥልነትን ሕይወት መተው ማለት ነው። ልብስ የሕይወት መሠረት አይደለም፤ ሊኾንም አይችልም። ጉዟችን ክርስቶስን ወደ መልበስ መኾን አለበት እንጂ በምድራዊ ጌጥ ማጌጥ መኾን የለበትም። ሕይወታችን መርዛማ ወደ መኾን እየተሸጋገረብን ያለው አንዱ በውጫዊ ልብስ ራሳችንን ለማስደነቅ የምንጓጓ በመኾናችን ነው። ስለዚህ ቅዱስ ዮሐንስ ጭንቀታችን የእግዚአብሔር መንግሥት የሚያስገኝ የንስሓ ሥራ መኾን እንዳለበት የአዋጅ ድምፁን አሰማን! የግመል ፀጒር መልበስ ማለት የበጋችን ክርስቶስን ለድኅነተ ዓለም አለመሸለት የሚያመለክት ነው። ዮሐንስ ወደ አማናዊው በግ መሪ እንጂ እርሱ ራሱ በጉ አይደለምና። የክርስቲያን እውነተኛ ልብስ ክርስቶስ ገና ታርዶ ከጥንተ በደል አላደነንም የሚለውን ምሥጢር አመልካች ነው።

==++=+=+++++=====+++====

ዮሐንስ ጌታቸው

11 Sep, 07:33


አንችልም። እንቍጣጣሽን የሚያከብሩ ነገር ግን ከእንቍጣጣሽ ሐሳብ ራቅ ያልን ስንት ነን? እጅግ ብዙ።

=======+++=+++=+==+==+==

እንቍጣጣሽ “ዕንቍ ለጣትሽ" የሚለውን የሚያመለክት ከኾነ፤ ለጣት አንገታችን ዕንቍ መስቀል ሊኖረው ይገባል። ግን ይኽን “በአንገታችን" ያለውን ዕንቍ መስቀላችንን ጭልጥ አድርገን ረስተነው ጭፈራ ቤት ይዘነው እንገባለን፤ በስካር ሰውነታችንን ሸብረክ ስናደርገው ዕንቍ ያለበትን መስቀል ዝቅ ዝቅ እናደርገዋለን። ይህ ድርጊታችን ዕንቋችንን አስረስቶ ብዙ ዘመን ኃጢአት ስንሠራ ኖርን። በአዲሱ ዓመት ከወደቅንበት እንውጣ ዕንቋችንን እናንሣ! ውጤቱ መራራ የኾነ የጨለማ ሕይወት ይብቃን፤ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ ሕይወት መኖር አንድ ብለን እንጀምር። ምንም እንኳን ዓመቱ ቍጥሩ ቢጨምርም ከእግዚአብሔር ጋር ኾነን ካልኖርን ለእኛ ቍጥሩም ዓመቱም አሮጌ ነው። እውነተኛ ሕይወት እግዚአብሔር ስለ ኾነ፣ ከእርሱ ውጭ ኾነው የሚኖሩት ሕይወት ኹሉ ሕይወት አይባልም፤ የሚቆጠረውም እንዳለመኖር ነው። ሕይወት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መኖር ማለት ነው። እንግዲያውስ የ2017 ዓ.ም ዕቅድዎት ምን ይኾን? እንደ ቀድሞ ባለመኖር ውስጥ ኾኖ መኖር ነው ወይስ ከእግዚአብሔር ጋር መኖር? ይህን ኹላችሁም ለራሳችሁ መልሱ።

“አዲሱን ዕንቍጣጣሽን ዕንቍ አያሳጣን"

https://t.me/phronema

ዮሐንስ ጌታቸው

11 Sep, 07:33


#######ዕንቍ_ጣጣሽ#######

===++=====+++========+==
የ2017 ዕንቍጣጣሽ ልዩ የሚኾነው በዕንቍጣጣሹ ውስጥ በሚንቆጠቆጠው ሰው አማካኝነት ነው። በእርግጥም የእንቍጣጣሽ "ዕንቍነት" በያዡ አያያዝ ላይ የሚመሠረት መኾኑን መረዳት ለማናችንም አይከብደንም። በኃጢአት እና በበደል በጠቆረው በዚያው ማንነታችን ኾነን ከያዝነው፥ እንቍጣጣሽ ለእኛ ውበት አይደለም ማለት ነው። እንቍጣጣሽ ውበትን የሚገልጥ መኾኑን ከተረዳን ልቡናችንን ውብ እናደርጋት ዘንድ ግድ አለብን፥ ያ የማይኾን ከኾነ እንቍጣጣሽ ወዴት አለ? እንቍጣጣሽ “መንቆጥቆጥን" ወይም ማማርን፡ መዋብን የሚያመለክት ስለ ኾነ፤ ከጥልቅ ውስጣች በበጎ ምግባራት መንቆጥቆጥ አለብን። እንደ በረዶ የነጣውን የንጽሕናን ተግባር መልበስና የንጽሕናን ሥራ ማሳየት አለብን። ኹል ጊዜ ሕይወታችንን በኦርቶዶክሳዊው ሕይወት የተንቆጠቆጠ ለማድረግ እጅግ መትጋት አለብን። የእግዚአብሔር መንግሥት የሚወረሰው በብዙ መከራና ሥቃይ መኾኑን ቅዱሳት መጻሕፍት ያስረዳሉና። አዲሱ ዓመት በእኛ ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት አዲስ ካልኾነ በቀር ምኑን ታደሰ!

=========+++======+====+

ብዙውን እድሜያችንን በእንቍጣጣሽ ሳይኾን የቆየነው በ " ዕንቍን አጣሽ" ሕይወት ነው። የሕይወት ዕንቍን ክርስቶስን ትተን “ዕንቍን አጣሽ" የተባለ ዲያብሎስን በማስደሰት ነው የኖርነው። ለዚህ ነው በእንቍ ጣጣሽ የዕንቍን አጣሽ ሥራ ስንሠራ የምንገኘው። ይህ በእጅጉ የሚያሳዝን ነው። በቀደመው ዓመትም ከእግዚአብሔር ይልቅ ዘፈንን በውስጣችን አንግሠን፡ በዲያብሎሳዊ ግብር ዓመቱን በርዘን የማያረጀውን አስረጅተናል። አኹንም እግዚአብሔር የሚሰጠንን አዲስ ዓመት ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጭ በኮንሰርት መርዘን ለመያዝ ተዘጋጅተናል። በእርግጥ ከእኛ በላይ የእኛ ጠላት ማን አለ? ራሳችን ከሰላም ውጭ ኾነን እግዚአብሔር ሰላም ካልሰጠን እያልን እንዘባበታለን! የሰላሙን ምንጭ ከልቡናችን ጥልቅ ገፍተን፥ የዓለምን ፍቅር በጥልቃችን አስገብተን በአዲሱም ዓመት አንድ ብለን ልንጨፍር፣ ልንዘፍን፣ ልንሰክር መዘጋጀታችን እጅጉን ያሳዝናል! በእንቍ ጣጣሽ “ዕንቋችን" ክርስቶስን በሕይወታችን ውስጥ መግለጥ አለብን። ዕንቍ የተባለን ጌታን ከሐዋርያት ጋር አግኝቶ ነገር ግን እንደ ፈሪሳውያን በግብዝነት ሕይወት ገፍቶ የማጣት “ጣ! ጣ!" ውስጥ እንዳንገባ ከቀደመው የበለጠ እንትጋ።

=====+++==++===========

እንቍጣጣሽ “እንቍጣጣሽ" የሚኾነው ዕንቍ ክርስቶስን የምናገኝበትን ሥራ ከግብዝነት ውጥተን ስንሠራ ነው። ዕንቋችን ክርስቶስን በዚህ ዓለም ርካሽ ፖለቲካ አማካኝነት “ጣጣ" አድርገው ከልባቸው ያጠፉ አሉ። በዚህ ዓለም ግሳንግስ ዘፈኑ፣ ተራ አስተሳሰብ፣ ራስ ወዳድነት፣ ዝሙትና መዳራት፣ ጥላቻና አረመኔያዊ ጭካኔ “ጣ! ጣ!" አድርገን ዕንቍ ወንጌልን ጥለን የምን እንቍ ጣጣሽን ማክበር ነው? ዕንቍጣጣሽ የሚከብረው በ"ዕንቍ" ወንጌል አማካኝነት መኾኑን ማን ባስታወሰን! ነፍሳችን የእግዚአብሔርን ቃል አጥታ በጽኑ ሕማም ውስጥ መኾኗን ገና አለመረዳታችን፡ ቃለ እግዚአብሔርን ካለመስማታችን በላይ ሌላ ጉዳት ነው። በበሽተኛ የሕይወት ምላሳችን ጥዕምት 2017 ዓ.ምን ልናመርራት ታጥቀናል። በጳጒሜን እንኳን እግዚአብሔር ዕድሜን የሚጨምርልን ወደ ልቡናችን እንድንመለስ ፈልጎ መኾኑን ዘንግተናል። የቀደመውን የጨለማ ሕይወት በብርሃን ወንጌል አማካኝነት አርቀን ወደ አዲስ አኗኗር እንዳንመጣ የቀደመው ልማዳዊ የኃጢአት ሕይወት አኹንም ገና እየጣመን ነው። አኹንም መልሳችን አንዴ ነው! ለበዓል ብቻ ነው! ዛሬ ዘና ፈካ ካላልኩ እስከ መቼ ልጨናነቅ! እያልን ለራሳችን ጥፋት ራሳችን የደከመ ምክንያት በማቅረብ እንስታለን።

==++=++++++==========++=
በእርግጥ እንቍጣጣሽ “ዕንቍን አመጣሽ" ከኾነ ከልባችን መዝገብ "ዕንቍ" መልካምነት መምጣት አለበት። ሕሊናችን በማስመሰልና በመገበዝ እሳት ተቃጥሎ አመድ አስተሳሰብ እንዳያመጣ መጠንቀቅ ይኖርብናል። ልባችንን “ልቤ ሆይ!" ዕንቍ ሰላምን አምጣልኝ እንጂ “ጣ! ጣ!" ጸብን አታምጣብኝ ከማለት እንጀምር። መልካምን በመምረጥ ካልጀመርን ዓመቱን የመልካምነት ቤት አድርገን መኖር አንችልም። ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ "መልካም የኾኑ ነገሮች ኹሉ ብንዘረዝር ከእርሱ የባሕርይ መልካምነት በጸጋ ያላገኘ ወይም ከእርሱ ያልተሰጠው መልካም ነገር በምድር ላይ የለም፤ ሊኖርም አይችልም። በቅዱሳት መጻሕፍት ተደጋግሞ እንደ ተገለጸው መልካሙ ኹሉ ከእርሱ የተገኘ ነው። መልካም ዘር የተባለው እርሱ ነው። መልካም መሬትም እርሱ የፈጠረው ነው። መልካም ፍሬን የሚያፈራው መልካም ዛፍም ኾነ ከልቡ መልካም ነገርን የሚያፈልቀው መልካሙ ሰው የእርሱ መልካምነት መገለጫዎች ናቸው። በአጠቃላይ 'እግዚአብሔርም ያደረገውን ኹሉ አየ፥ እነኾም እጅግ መልካም ነበረ" ዘፍ 1፥31 ተብሎ እንደተጻፈ ያለ እርሱ መልካም ነገር የለም፤ ሊኖርም አይችልም። ይህን የሚያውቁ ደግሞ ራሳቸውን መልካም መሬት አድርገው መልካሙን ዘር ተቀብለው መልካም ፍሬ ያፈራሉ። መልሰውም ከጎተራቸው መልካሙን ዘር አውጥተው እንደገና ይዘራሉ። በርግጥም መልካም ነገር አንድ ነው።" ይላል። (ግርማ ባቱ (መምህር)፣ የነገረ መለኮት መግቢያ፣ 2013 ዓ.ም፣ ገጽ 2-3)። ስለዚህ በመልካምነት ያልያዟት እንቍጣጣሽ ጣዕም አልባ ናት።

====+++=+++=+++=======+=

ይህ አዲስ ዓመት የቅድስት ቤተክርስቲያን “ዕንቍ ጣጣዋ" መኾን አለበት። ዕንቍ የተባሉ የምእመናንን መከራና ሥቃይ፣ ስደትና ረሃብ ጣጣዋ ሊኾን ይገባል። ፍትህ ርትዕ የተባለው ዕንቍዋ፥ ሰላሟን በሚሰብረው መንግሥታዊ አሠራር ሊመጣላት ባይችልም ወደ ዕንቍ ክርስቶስ ድምጿን ከፍ አድርጋ በማሰማት ርቱዕ ሰላምን ለልጆቿ ማፍሰስ አለባት። የቤተክርስቲያን ጣጣዋ (ፍላጎቷ) ዕንቍ (ሰላም፣ ፍቅር፣ አንድነት፣ የመሳሰሉትን) ላለማጣት መትጋት መኾን ነው ያለበት። የቤተ ክርስቲያን ሰላሟ ምን እንደ ኾነ በልጆቿ ልቡና ውስጥ መቅረጽ አለባት። ያኔ ዓመቱ በምእመናን ልቡና ሰላሟ የሚፈስባቸው አዲስ ዓመት ይኾናል። በእርግጥ ይህም የሚጀምረው ከእኛው ነው። የመጀመሪያዎቹ የእኛው ሰላም ባለቤቶች እኛው ነንና። እያንዳንዳችን ለእያንዳንዳችን ሰላምን ለማምጣት ከጣርን ሰላማችን አንድ ዓይነት ኾኖ ዓመታችን የጋራ ሰላማችን ምንጭ ሰላማዊ ይኾናል። እርስ በእርስ ስንጨካከንና ስንጠላላ፤ ከፈቃደ እግዚአብሔር ይልቅስ የየግል ስሜታችንን የሕይወታችን መርሕ ስናደርግ እውነተኛውን ሰላም ማግኘት ያቅተናል። ሰላሙን ስናጣና ተስፈኝነት ይጠፋናል፣ ጭንቀትና ፍርሓት ይጋርደናል። ይህ ደግሞ ሕይወታችንን ባልተገባ ክፉ ኀዘን ሰቅዞ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንድንኖር ያደርገናል። ይህ ከኾነ ዕንቍ ጣጣሽ ወዴት አለ?

====++====+++=====++====
እንቍጣጣሽን በዚህ ዓለም ተራ ማስክ (የዘረኝነት፣ የጥላቻ፣ የልዩነት፣ የረብሽና የመሳሰሉትን) ሸፍነን ጣጣ ውስጥ እንዳንገባ። ማስኩን የምንጠቀመው ኮሮናን ለመከላከል እንጂ ዕንቋችንን ለማራቅ መኾን የለበትም። ከልባችን የሚመነጨው የኃጢአት ጎርፍ በሰውነታችን ላይ ጎርፎ ጥርግርግ አድርጎ እንደ ወሰደን ማወቅ ሲያቅተን ቆሻሻው ሐሳባችን የሚወጣበትን አፍ “በማስክ" ሸፈነው። ኾኖም ግን አኹንም ያሸፈነንን ኮሮናን (ቆሻሻ ሐሳባችንን) ከፈት እያደረግን ማስወጣታችንን አላቆምንም። እንግዲህ በዚህ መንገድ ወደ እንቍጣጣሽ ውስጥ መግባት አንችልም። ወደ እንቍጣጣሽም መድረስ

ዮሐንስ ጌታቸው

10 Sep, 14:33


+++++++++#እስከ_መቼ#+++++++++

ኢትዮጵያውያን የቀደመውን የኢትዮጵያዊነት መልካም እሴት ትተን በማስመሰልና በከንቱ ሕይወት የምንቀጥለው እስከ መቼ ነው? ፖለቲከኞች በራሳቸው ልክ ሠርተው የሚያቀርቡልንን የሐሰት ትርክት እየሰማንና ሲያሻንም አንዳንዱን እውነት አድርገን እየወሰድን በተግባራዊ ሕይወታችን የጥላቻን ጎርፍ የምናጎርፈው እስከ መቼ ነው?

ፖለቲከኞች ውሸትን ልባቸው አድርገው ከውሽት ልቡናቸው ውስጥ የሚያፈሱትን የመንገድ ውኃ እየጠጣን፤ ከእነርሱ ባላነሰ መንገድ በፈጣሪያችን ላይ እየቀለድን የማስመሰልንም ሕይወት መሥዋዕት አድርገን የምናቀርበው እስከ መቼ ነው?

ፖለቲከኛው፣ ዘረኛው፣ ሐሰተኛው ነቢይ፣ ሌባውና አስመሳዩ እኛን የሚያታልለን በአግባቡ ስለማንመረምርና በውስጣቸው ደብቀው የያዙትን አጀንዳ ያልተረዳን መኾናችንን አውቀው ነው። ስለዚህ ድንቁርናችንን በር አድርገው ወደ ሕሊናችን ገብተው የሚያቃጥሉን እስከ መቼ ነው? እጃችንን ለጸሎት አንሥተን ልባችንን ኃጢአት ባለበት ቦታ የምናስቀምጠው እስከ መቼ ነው?

አንተ ልክ አይደለህም! አንቺም ልክ አይደለሽም እያልን አስተያየት የምንሰጠው ነገር ግን እግዚአብሔር ከሚፈቅደው እውነተኛ ሕይወት ውጭ በኃጢአት ጨለማ ውስጥ የምንኖረው እስከ መቼ ነው?

ክፉን በወቀስንበት ልክ በእግዚአብሔር ላይ የከፋውን የእኛን ሕይወት የማናስተካክለው እስከ መቼ ነው? እስከ መቼ ድረስ ልባችን ግትር ኾኖ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ባለመፈጸም ይጓዝ ዘንድ እንፈቅድ ይኾን?

መንግሥት ከሚያታልለን ይልቅ የማይታለለውን አምላክ እኛው ለማታለል የሄድንባቸው መንገዶች አይከፉም ይኾን? መንግሥት ለራሱ ድጋፍ ፈልጎ ያልኾነውን ኾነ የኾነውን አልኾነ እያለ የሐሰት ትርክቱን በሚዲያ ከሚያቀርበው ይልቅ በአርአያው የፈጠረንን አምላክ በሰውነት ሚዲያችን አላከብርህም ብለነው የምናቀርበው የኃጢአት ትርክቶች አይበልጡምን? እስከ መቼ እንዲህ እንኖራለን?

ክፉዎች ያቃጠሏቸው አብያተ ክርስቲያናትን አይተን ልክ አይደለም ብለን እንደ ምናወግዘው ኹሉ ዋናውን የእግዚአብሔር መቅደስ ሰውነታችንን በትዕቢት እሳት የምናቃጥለው እስከ መቼ ነው? እስከ መቼ ነው በኃጢአት ላይ ኃጢአት እየፈጸምን የምንኖረው? እስከ መቼ ነው እንወዳታለን የምንላትን ቤተክርስቲያን “ሰውነታችንን" በዘፈን፣ በጭፈራ፣ በስድብና በጥላቻ፣ በዝሙትና መዳራት በመሳሰሉት እሳቶች እያቃጠልን የምንኖረው?

የእኛን ቤተ ክርስቲያን ማቃጠል እስካላቆምን ድረስ የቤተክርስቲያን ቃጠሎ ቆመ! ማለት አንችልም። መቅደስ ሰውነታችንን ክርስቶስ የተባለው አማናዊው እጣን እንዲሸተትበት እስካላደረግን ድረስ ቤተ ክርስቲያን መሰደቧ አይቀርም። መጀመር ያለብን እኛው እኛን ከማስተካከል ነው። እኛ ከተስተካከልን ማንም ምንም አያደርገንም። ወደ ኦርቶዶክሳዊ አስተሳሰብና ሕይወት እንመለስ! በርቱዕ እምነት ርቱዕ የኾነ ኦርቶዶክሳዊ አነጋገር፣ አስተሳሰብና አተያይን አጽንተን መያዝ እንጀምር።

አዲሱ ዓመት የድንቁርና ጉዟችን ቆሞ! እግዚአብሔርን ከልባችን የምናገኝበትና ከእርሱ ጋር በደስታ የምንኖርበት ዘመን የሚኾነው እርሱን ለማግኘት ስንተጋ ነው። ማስመሰላችንን ከቀጠልን የሚያስመስሉብንም ይቀጥላሉ! እኛ ኹላችን ከማስመሰል ከወጣን ሊያስመስሉብን የሚያስቡ አካላት ማስመሰል አቅቷቸው ያቆሙታል። እኛ እነርሱን የምናሳየውን ነው እነርሱም እኛ ላይ የሚያደርጉት። ሁላችንም ፍቅርን ለማሳየት ከተነሣን ጥላቻን ይዞ የመጣውን መንገዱን መቀየር እንችላለን። የልዩነትና የዘረኝነት ሐሳብ ይዞ የሚመጣውን የአንድነትን ነገር በተደጋጋሚ ብናሳየው ከስሑት ሐሳቡ ይመለሳል። ስለዚህ አዲስ ዓመት ሲመጣ ያረጀንባቸውን የክፋት እሳቤዎች መተው እንዳለብን እንረዳ። የእግዚአብሔር ምሕረትና ይቅርታ እንዲጎበኘን በልባዊ ይቅርታ ዘመኑን እንጀምረው። በምንም ዓይነት ክፉ አስተሳሰብ ውስጥ ያለን ሰው ብናገኝ እግዚአብሔር በዚያ ሰው ላይ የሚያደርጋትን ምሕረት እናስብ። ይህንስ ለምን አያጠፋውም ወደሚል የሕሊና ፈተና ውስጥ ላለመግባት ከመጣር ጋር እውነቱን ወደ መረዳት አምጣው ብለን በፍቅር እንጸልይለት።

እግዚአብሔር አምላካችን ከልዩነትና 2016 ዓመተ ምሕረትን ካቆሸሸብን የዘረኝነት፣ የግድያ፣ የጭካኔ፣ የርኲሰት በሽታ በቸርነቱ ነጻ ያውጣን። አዲሱንም ዓመት በእርግጥም የምሕረት አድርገን እንድንኖረው ኃይሉን ያድለን። መልካም አዲስ ዓመት ይኹንላችሁ።

https://t.me/phronema

2,283

subscribers

73

photos

21

videos