TMA (Traffic Management Authority) @trafficmanagementagency Channel on Telegram

TMA (Traffic Management Authority)

@trafficmanagementagency


Work With Us / 'ከኛ ጋር ይስሩ'

TMA (Traffic Management Authority) (English)

Are you someone who is passionate about improving road safety and reducing traffic congestion? Look no further than the Traffic Management Authority (TMA) Telegram channel!
TMA is a dedicated team of professionals working towards ensuring smooth traffic flow, effective management of road networks, and the safety of all road users. They collaborate with government agencies, local authorities, and other stakeholders to achieve their mission of creating a more efficient and safer transportation system.

The Traffic Management Authority channel on Telegram, with the username 'trafficmanagementagency,' provides valuable insights, updates, and tips on traffic management, road safety, and related topics. By following this channel, you can stay informed about the latest developments in traffic management technology, road infrastructure projects, and best practices in traffic control.

Whether you are a transportation professional, an urban planner, a road user, or simply someone interested in the field of traffic management, this channel is perfect for you. Join the TMA community on Telegram and be part of the conversation on how we can all work together to make our roads safer and more efficient for everyone.

Don't miss out on this opportunity to connect with like-minded individuals, share your ideas, and stay updated on the latest trends in traffic management. Work with us at TMA and let's make a difference on the roads together!
Join us today by following 'trafficmanagementagency' on Telegram!

TMA (Traffic Management Authority)

07 Feb, 07:00


በካዛንቺስ መልሶ ማልማት ሂደት'
✿ የመንገድ ኔትወርኩን ይበልጥ ማስተሳሰር፣
✿ የመንገዶቹን ደረጃ ማስጠበቅ፣
✿ በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት አሰጣጥን ለማሳለጥ የሚረዱ መሰረተ ልማቶችን ከመሬት በታች መዘርጋት እና፣
ሌሎች የመልሶ ማልማት ስራዎችን ለዘላቂ ልማት ምቹ የማድረግ ስራ በመከናወን ላይ ይገኛል::

TMA (Traffic Management Authority)

07 Feb, 06:22


ዳይሬክቶቱ የበጀት ዓመቱን የ6 ወራት ስራ አፈፃፀምና የቀጣይ ግማሽ ዓመት በተከለሰ ዕቅድ ዙሪያ ተወያየ
*****
(ት/ማ/ባ ጥር 29/2017 ዓ.ም):- በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የመንገድ ፈንድ አስተዳደር እና ጉዳት ካሳ ዳይሬክቶሬት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት ስራ አፈፃፀም እና የቀጣይ ግማሽ ዓመት በተከለሰ ዕቅድ ዙሪያ ከ11ዱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ከተውጣጡ የመንገድ ፈንድ ባለሙያዎች እና የኩነት ቡደን መሪዎች እንዲሁም ከማእከል ከሁሉም የስራ ክፍል ሃላፊዎች ጋር በዛሬው እለት ተወያይቷል፡፡

የውይይቱን በንግግር የከፈቱት በባለስልጣ መ/ቤቱ ምክትል ዋና ዳይሬተር አቶ አማረ ታረቀኝ የመድን ፈንድ እና ጉዳት ካሳ ዳይሬክቶሬት ስራ ከጀመረ አጭር ጊዜ ቢሆነውም የቅድመ አደጋ እና ድህረ አደጋ መከላከል ዙሪያ ተግባራትን አከናውኖ የሚታይ ውጤት እንዳስመዘገበ። ተናግረዋል፡፡

ለዚህም ከሁሉም ክልሎች አንደኛ በመውጣት ተሸላሚ መሆኑን የጠቀሱት ም/ዋና ዳይሬክተሩ ለውጤቱ መገኘት የደከሙትን በሙሉ አመስግነዋል፡፡

በቀጣይም በሙሉ መዋቅር የተሻለ ስራ ለመስራት የሚያስችል አቅምም ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ 

በክፍሉ ባለሙያ የስድስት ወር አፈፃፀም ሪፖርት ገለፃ የተደረገ ሲሆን የመንገድ ፈንድ አስተዳደር እና ጉዳት ካሳ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አብይ ገ/ሚካኤል የቀጣይ ግማሽ ዓመት የተከለሰ እቅድ አቅርበዋል፡

በመጨረሻም በቀረቡት ሁለቱ ሰነዶች እና አጠቃላይ በስራ ወቅት በነበሩ ጉዳዮች ዙሪያ የውይይቱ ተሳታፊዎች ጥያቄዎችና እሰተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን ከመድረኩም ምላሽና ማብራሪያ ተስጥቶበታል፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

06 Feb, 13:12


በሁለተኛው ምእራፍ የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት ምን እየተከናወነ ነው?

• ሁለተኛው ምእራፍ የኮሪደር ልማት ስራ በአዲስ አበባ በ8 አካባቢዎች እየተከናወነ ነው።
• በሁለተኛው ምእራፍ የሚከናወነው የኮሪደር ልማት በአጠቃላይ 2 ሺህ 879 ሄክታር መሬት የሚሸፍን ሲሆን፤ 240 ኪሎ ሜትር የአስፋልት እንዲሁም 237 ኪሎ ሜትር እግረኛ መንገድ በመገንባት ላይ ነው።
• በስምንቱም የኮሪደር ልማት ስፍራዎች 32 የህጻናት መጫዎቻዎች ፤ 79 የሚሆኑ ህዝብ መዝናኛ ስፍራዎች እንዲሁም 114 የመኪና መቆሚያ ፓርኪንግና የታክሲና አውቶብስ ተርሚናሎችን ያከተተ መሰረተ ልማት ይከናወናል።
• ከትራንስፖርት መሰረተ-ልማቶች መካከል 58 በሚሆኑ አካባቢዎች ላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቻርጅ ጣቢያዎች ይኖራሉ።
• ከ100 ኪሎ ሜትር በላይ የሚሆን የብስክሌት መንገድም በመገንባት ላይ ነው።
• የከተማዋ ነዋሪዎች ጤናቸውን የሚጠብቁባቸው 17 የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችም ተገንብተው ለአገልግሎት ክፍት ይደረጋሉ።
• በኮሪደር ልማት ስራው ከእንጦጦ -ቀበና-ግንፍሌ ፒኮክ እንዲሁም ከእንጦጦ-ወዳጅነት-ፒኮክ የሚደርሱ ሁለት የወንዝ ዳርቻ ልማት ስራዎችም እየተከናወኑ ነው። የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት

TMA (Traffic Management Authority)

06 Feb, 12:07


አበባ ትምህርት ቢሮ በህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ስራዎች ዙሪያ ልምድ ልውውጥ ተካሄደ
**********************
(ት/ማ/ባ ጥር 29/2017 ዓ.ም) ፡-የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰራተኞች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራዎችን በአካል በመጎብኘት የልምድ ልዉዉጥ አካሂደዋል፡፡
ባለስልጣን መ/ቤቱ እንደ ባለድርሻ አካል የትራፊክ ደህንነትን ለማረጋገጥ በቅንጅት ተግባራትን ከሚፈጽመው ተቋማት መካከል የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አንዱ ነው በመሆኑም የህዝብ ግንኙነትንና ኮሙዩኒኬሽን ስራዎችን ለማጎልበትና ለማስፋትም የተሞክሮ ልውውጥ ተደርጓል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ቸርነት ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለመጡ ሰራተኞች በክፍላቸው በሚሰሩ የስነተግባቦት ስራዎች ላይ ገለጻ አድርገዋል፡፡
በተለይም ስራዎቹን ተደራሽ የሚያደርጉበት የማህበራዊ ሚዲያ ፕላት ፎርሞቹን በተጠናከረ መልኩ እንደሚጠቀሙባቸው የገለጹት አቶ አበበ ዘመኑም የቴክኖሎጂ በመሆኑ ስራዎቻቸውን ህብረተሰቡ ጋር ለማድረስ ፕላት ፎርሞቹ ከፍተኛ እገዛ እንዳረጉላቸው ተናግረዋል፡፡
አክለዉም የህትመትና የፕሮዳክሽን ስራዎችን ለመስራት አስፈላጊዉ ግብዓትና በጀት ከቢሮው እንደሚመደብ ገልጸዉ ስራዎች በተፈለገዉ ግዜ ተደራሽ መሆናቸዉም የማህበራዊ ሚዲያ ተከታዮች ቁጥር በየጊዜዉ እየጨመረ እና ተሳትፎም እየላቀ መምጣቱን አስረድተዋል፡፡
በመጨረሻም ልምድ ለመቅሰም በቦታው የተገኘው የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ሰራተኞች ቡድንም ባገኙት ተሞክሮ በተለይ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚከወኑ ተግባራትን አጠናክረው እንደሚሰሩበት አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ለተደረገላቸዉ አቀባበል እና ሰፊ ማብራሪያም ቢሮዉን እና የስራ ክፍሉን አመስግነዉ መሰል መድረኮችን በመፍጠር ግንኙነቱን እንደሚቀጥሉበት ጠቁመዋል፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

03 Feb, 12:57


ዲጂታል(ፋይዳ) መታወቂያ አተገባበር፣ አጠቃቀም እና የተፈፃሚነት ወሰንን የተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
*****************
(ት/ማ/ባ ጥር 26/2017 ዓ.ም)፡- በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ከብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ጋር በመተባበር በአብሮነት መርሃ ግብር ላይ የዲጂታል(ፋይዳ) መታወቂያ አተገባበር፣ አጠቃቀም እና የተፈፃሚነት ወሰንን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለዋና መ/ቤት ሰራተኞች በዛሬው እለት ሰጥቷል፡፡
መርሃ ግብሩን በንግግር የከፈቱት በባለስልጣን መ/ቤቱ የአስተዳርና ፋይናንስ ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ ሐዋ ዋቢ እንደተናገሩት እንደ ሃገር በየዘርፉ የተጀመረው እና እየተተገበረ የሚገኘው የሪፎርም ስራ በተለይም ለዜጎቻችንን የአገልግሎት አሰጣጥ ስርዓቱን ለማሻሻል እንዲያስችል ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ መንገድ ጠርጎልናል፡፡
በተለይም ይህን እንደ ሃገር የተያዘውን የዲጂታላይዜሽን ውጥን የሚያግዘውን የፋይዳ መታወቂያ አሰጣጥ ስርዓት ወደ ከተማ አስተዳደሩ ማህበረሰብና መንግስት ሰራተኛው በማውረድና ሁሉም የዲጀጂታል/ፋይዳ መታወቂያ እንዲወስዱ በማስቻል ውጤት ላይ መድረስ አስፈላጊ ነው ሲሉም ሃላፊዋ ተናግረዋል፡፡
በመርሃ ግብሩም ሁሉም ሰራተኛ ስለመታወቂያው ምንነትና አስፈላጊነት በእኩል ግንዛቤ አግኝቶ ራሱም ሆነ ወገኖቹ መታቂያውን በመያዝ አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ የተዘጋጀ እንደሆነም ተመላክቷል፡፡
በብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የህግና ፖሊስ ክፍል ሃላፊ ወ/ሮ ገብርኤላ አብርሃም በበኩላቸው ፕሮግራሙ ከተጀመረ ወዲህ 11.5 ሚሊየን ሰው እንደተመዘገበና በ2020 እንደ አገር 90 ሚሊየን ህዝብ ለመመዝገብ መታቀዱን አስታውቀው ከመስከረም ወር ጀምሮ በአዲስ አበባ ምዝገባው እንደተጀመረ ገልጸዋል፡፡
ፕሮግራሙ በአሁኑ ወቅት ከ50 በላይ ተቋማት ጋር ትስስር እንደተፈጠረ ገልጸው የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣንም እንደ አንድ ባለድርሻ አካል በመውሰድ በዛሬው እለት ለሰራተኛው የዲጂታል(ፋይዳ) መታወቂያ አተገባበር፣ አጠቃቀም፣ የተፈፃሚነት ወሰንና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በመጨረሻም የዲጂታል/ፋይዳ መታወቂያን አስመልክቶ ከስልጠናው ተሳታፊ አስተያየት እና ጥያቄዎች ቀርበው ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶበታል፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

03 Feb, 06:07


ይህ ለቡ መብራት ኃይል አካባቢ የደረሰ የትራክ አደጋ ነው፡፡ አሽርካሪዎች በመዝግታ እና በማስተዋል ያሽከርክሩ❗️

TMA (Traffic Management Authority)

03 Feb, 05:48


🚦 እግረኛውም ሆነ አሽከርካሪው ትክክለኛ የመንገድ አጠቃቀም በመጠቀም ራሱንና ወገኑን ከትራፊክ አደጋ ይጠብቅ::

🤞 መ/ቤታችን መልካም ጉዞ፤ ፍሬያማ የስራ ቀን ይመኛል❗️❗️

TMA (Traffic Management Authority)

03 Feb, 05:42


አሽከርካሪዎች ከቤታችን ስንወጣ የጎግል ማፕ (Google Map) መተግበሪያ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በከተማዋ መንገዶች ላይ ያለውን የትራፊክ ፍሰት ሁኔታን ማወቅ ባህላችን እናድርግ::
ቀዩ መስመር ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳለ የሚያመለከት ሲሆን ቢጫው መካከለኛ አረንጓደው ደግሞ መንገዱ ነጻ መሆን የሚጠቁም ሲለሆነ በዚሁ ልክ ይጠቀሙ!
መልካም የስራ ሳምንት!!!

TMA (Traffic Management Authority)

29 Jan, 07:16


ስልክ እየተጠቀሙ/እየነካኩ ማሽከርከር ለአስከፊው የትራፊክ አደጋ ያጋልጣል📵❗️

TMA (Traffic Management Authority)

29 Jan, 07:05


ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በዕቅድ አፈጻጸም እና በትራፊክ አደጋ ንጽጽር ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ግምገማዊ ውይይት አካሄደ
 (ት/ማ/ባ ጥር 21/2017 ዓ.ም)፡- የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወር ዕቅድ አፈጻጸም እና በትራፊክ አደጋ ንጽጽር ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ግምገማዊ ውይይት በጽ/ቤቱ በዛሬው ዕለት አካሄደ፡፡ 
የዕቅድ አፈጻጸሙን ሪፖርት ያቀረቡት የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመንገድ ደህንነት ግንዛቤና ደንብ ማስከበር ዳይሬክቶሬት አቶ ገዛኽኝ ታምሩ እንደተናገሩት በስድስት ወር ውስጥ በተከናወኑ ተግባራት ከተገኙ ውጤቶች መካከል በመንገድ ላይ የሚከናወኑ ሕገ ወጥ ኩነቶችን መቀነስ መቻሉ፣ በሃይማኖታዊ በዓል አከባበር ወቅት ምዕመናን ላይ የሚደርሰውን የትራፊክ አደጋ መቀነስ፣ በተለይ በትምህርት ቤቶች አካባቢ የእግረኞች የመንገድ አጠቃቀም መሻሻሉ ፣ አደባባይ ላይ የሚቆሙ ተሽከርካሪዎችን በማንሳት የትራፊክ መጨናነቅን መቅረፍ መቻሉ፤በአጠቃላይ  በመንገድ ተጠቃሚዎች ዘንድ  የሕግ ተገዥነት መሻሻል ማሳየቱ የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
እንደ አቶ ገዛኽኝ ሪፖርት ከባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት መሠራቱ፣ አልኮል ጠጥቶ በማሽከርከር፣ በእግረኛ እና በፍጥነት ቁጥጥር ላይ በፕሮግራም እየተሠራ መሆኑ በጠንካራ ጎን ከሚነሱ መካከል የሚጠቀሱ ሲሆን የባለሙያ አለመሟላት እና የግብዓት እጥረት ካጋጠሙ ችግሮች መካከል መሆናቸው ተመላክቷል፡፡ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ተብለው ከተቀመጡት ከባለድርሻ አካላት ጋር የበለጠ ተቀናጅቶ መስራት፣ ከአቻ ተቋማት ጋር የልምድ ልውውጥ በማድረግ ተሞክሮን መጠመርና ማስፋት እንዲሁም የትራፊክ ፍሰትና ደህንነትን የሚያሻሽሉ ምልክቶችን በጥናት በመለየት ማሻሻል የሚሉት ይገኙባቸዋል፡፡
በውይይቱ ላይ አስተያየታቸውን የሰጡ የጉለሌ ክፍለ ከተማ የትራፊክ የሕዝብ ግንዛቤና የአባላት ሙያ ማሳደግ ማስተባበሪያ ኃላፊ  ኢንስፔክተር ደምስ ማሞ እንደተናገሩት በዕቅዶች ላይ ተቀናጅቶ መሥራት ውጤታማ ያደርጋል ብለዋል፡፡ አቶ ደሱ አሰፋ ከአዲስ አበባ አውቶቡስ አገልግሎት ድርጅት እንደተናገሩት የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከባለድርሻ አካላት ጋር መሥራት በመቻሉ የትራፊክ መጨናነቅ እንዲቀንስ አድርጓል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም በቀረበው ሪፖርት ላይ ባለድርሻ አካላቱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የቀረቡ ሲሆን  የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሕይወት ታደሠ እንደገለፁት ውይይቱ ዓላማውን ያሳካ ሲሆን የተገኙ ውጤቶችን አጠናክረን በማስቀጠል በቀጣይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተባብረን እንሠራለን፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

27 Jan, 14:57


ባለሥልጣን መ/ቤቱ በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስደስት ወራት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ያከናወናቸው ተግባራት ውጤታማ መሆናቸውን ገለፀ
*****
( ት/ማ/ባ ጥር 19/2017 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን በበጀት አመቱ ስድስት ወራት ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን ያከናወናቸው የመንገድ ደህንነት ማሻሻያ ሥራዎች በትራፊክ ፍሰትና ደህንነት ላይ የተሻለ ውጤት ማስመዝገቡን አመላክቷል፡፡

በባለስልጣን መ/ቤቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ክትትል ድጋፍና ምዘና ዳይሬክቶሬት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስደስት ወራት የስራ ክንውን ሪፖርት ሰነድ ላይ እንዳመለከተው መንገዶች ለእግረኞች ምቹ ሆነዋል፤ ከ500 በላይ ተማሪ ትራፊክ ፖሊሶችን ማሠልጠን ተችሏል፤ ከ50 ሺህ በላይ በሚሆኑ የትራፊክ ደንብ ተላላፊዎች ላይ የእርምት ርምጃ ተወስዷል፤ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ እንዲደገፉ ተደርጓል እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ የተሽከርካሪ ማቆሚያ ቦታዎችን ማልማት ተችሏል፡፡

በተለይም በከተማ ደረጃ በ10 ቦታዎች (መጋጠሚያዎች፣ አደባባዮችና መንገዶች ላይ ማለትም (ለገሃር፣ ጀርመን፣ ቀበና፣ ዲያስፖራ፣ ሳህሊተ ምህረት፣ የቀድሞ፣ ኢቲቪ፣ ኢሊያና፣ አልማዚዬ፣ ኮተቤ BRT እና ጀሞ BRT መጋጠሚያዎች) የመብራትና የቀለም ማሻሻያ ሥራ በማከናወን የመንገድ ደህንነትና ፍሰት ከማሻሻል አንፃር ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡

ባለስልጣን መ/ቤቱ በዝግጅት ምእራፍ በዓመታዊ ዕቅዶቹ ዙሪያ ከ18 ባለድርሻ አካላት ጋር በመወያየትና እቅዱንም የጋራ በማድረግ የትስስር ሰነድም በመፈራረም ሥራዎችን ለክቶና ሰፍሮ ለባለድርሻ አካላቱ መስጠቱም ተጠቁሟል፡፡

በዚህ አግባብ በትግበራ ምዕራፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በከተማ ደረጃ በቅንጅት ለመሥራት የታቀዱ ተግባራት የሥራ አፈጻጸም ከታቀደው በላይ መከናወኑን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የአገልግሎት አሰጣጥ ክትትል ድጋፍና ምዘና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጎይቶም አስፋው ገልፀዋል፡፡

ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንና ከትምህርት ቢሮ ጋር ተባብሮ በመሰራቱ ከተገኙ ውጤቶች መካከል በከተማ ደረጃ በበጀት ዓመቱ ለትራፊክ አደጋ ተጋላጭ የሆኑ 84 ትምህርት ቤቶችን በጥናት በመለየት 550 አዳዲስ ረዳት የተማሪ ትረፊክ ፖሊሶችን አሠልጥኖ በሥራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት ላይ ተማሪዎችን በማሻገርና ግንዛቤ በማስጨበጥ ሥራ እንዲሰማሩ ተደርጓል፡፡

እንዲሁም የመንገድ ደህንነት ጽንሰ ሃሳብ በመጀመሪያ ደረጃ (ከ1-8ኛ ክፍል) ሥርዓተ ትምህርት ውስጥ በማካተት በ4 የተለያዩ የትምህርት ዓይነቶች እንዲሰጥ በማድረግ በትምህርት ቤቶች አካባቢ ሲደርሱ የነበሩ የትራፊክ አደጋዎችን መከላከል መቻሉን አቶ ጎይቶም አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩልም ከደንብ ማስከበር ቢሮ ጋር በመሆን በከተማ ደረጃ 119 ሕንፃዎች ላይ የተለያዩ አስተማሪ የሆኑ አስተዳደራዊ ርምጃዎችን በመውሰድ የገንዘብ ቅጣት እንዲጣል በማድረግ (11,000,900.00 ብር) መሰብሰቡ ፣145 ሕንፃዎች የብቃት ማረጋገጫ ወስደው ወደ ሥራ እንዲገቡ እና የሕንፃ ሥር ተሽከርከሪ ማቆሚያ ቦታዎቻቸውን ለታለመላቸው ዓላማ እንዲያውሉ ማድረግ መቻሉ ተገልጿል፡፡

አቶ ጎይቶም የስድስት ወር የባለድርሻ አካላት ሥራ አፈጻጸም በመገምገም በቀጣይ ስድስት ወር ውጤታማ ሥራዎች የሚሠሩ እንደሆነ ጠቅሰው ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ጠቁመዋል፡፡

በኤልያስ ተስፋዬ
ፎቶ በአማረ ጠገናው

TMA (Traffic Management Authority)

24 Jan, 11:52


አዲሱ የመንገድ ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 ዙሪያ የጎዳና ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ተከናወነ
**********************
(ት/ማ/ባ 16/05/2017 ዓ.ም):- በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የአራዳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ እና ደንብ ማስከበር ዳይሬክቶሬት ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ትራፊክ ዲቪዚዮን እና የበጎ ፍቃደኛ ትራፊክ አስተናባሪ ወጣቶች ጋር በመተባበር በአዲሱ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ደንብ ዙሪያ ለአሽከርካሪዎች እና እግረኞች የጎዳና ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ተሰጠ፡፡
የግንዛቤ ማስጨበጫው በዋናነት ህዝብ በሚበዛባቸው ቦታዎች መካከል ከጎዮርጊስ ቤተክርስቲያን እስከ በዮሐንስ ቤተክርስቲያን እንዲሁም በድሮው አትክልት ተራ ባለው የታክሲ ተርሚናል አካባቢ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ተሰርቷል።
ግንዛቤ ንቅናቄው ትኩረቱን ያደረገው በአዲሱ የመንገድ ትራፊክ መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 557/2016 ዙሪያ አሽከርካሪዎች የሚኖርባቸውን ብዥታ ሊያጠራ በሚችል መልኩ ግንዛቤ እንዲያገኙ ነው። በተለይም አሽከርካሪዎች የጥፋት አይነቶችንና፣ ለጥፋቶቹ የሚቆጠር የቅጣት ነጥቦችን የሚገልጽ በራሪ ወረቀቶች ተደራሽ ሆነዋል። ይህ መደረጉ አሽከርካሪዎች ደንቡን በሚገባ ተገንዝበው መብትና ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ያስችላቸዋል፡፡ የመንገድ ተጠቃሚዎች ተገቢ የመንገድ አጠቃቀም ስነ-ስርዓት በመከተል እራሳቸውን እና ሌሎችን ከትራፊክ አደጋ እንዲጠብቁ ሰፊ ግንዛቤ ስራ ተሰርቷል፡፡
በአዲሱ የመንገድ ትራፊክ ቁጥጥር ደንብ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ላይ በራሪ ወረቀቶች ተሰራጭቷል፤ በአሽከርካሪ ላይ የድምጽ ማጉያዎች ግንዛቤ ለአሽከርካሪዎች እና ለእግረኞች ተፈጥሯል፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

23 Jan, 12:50


የተሽከርካሪ አገልግሎት አሰጣጥ ደንብ ቁጥር 165/2016 ወደ ስራ በመገባቱ ባለፉት 6 ወራት 145 ህንጻዎች የህንጻ ስር ፓርኪንግ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸው ተገለጸ
•  ለ2,490 ተሸከርካሪዎችም የመቆሚያ ቦታ ተገኝቷል
(ት/ማ/ባ ጥር 15/2017 ዓ.ም) ፡- የተሽከርካሪ አገልግሎት አሰጣጥ ደንብ ቁጥር 165/2016 ጸድቆ ወደ ስራ በመገባቱ በበጀት ዓመቱ 6 ወራት 145 ህንጻዎች የህንጻ ስር ፓርኪንግ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን  በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የፓርኪንግ መሰረተ ልማትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት አስታውቋል፡፡
ዳይሬክተሩ አቶ ቢኒያም ጌታቸው እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት 249 ህንጻዎች መሉ የፓርኪንግ አገልግሎት እየሰጡ በመሆናቸውም 2,490 ተሽከርካሪዎች ከዋና መንገድ ላይ ማንሳት ተችሏል፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የፓርኪንግ መሰረተልማት ፍላጎትን ለመጨመር እና ፍሰቱን ሰላማዊ ለማድረግ የሚያከናዉን ተግባር ደንቡ ምቹ ሁኔታን እንደፈጠረለት የገለጹት ዳይሬክተሩ በከተማዋ ከ4 ወለል በላይ ያላቸዉ ህንጻዎች የህንጻ ስር ፓርኪንግ እንዲያመቻቹ የምዝገባ እና የቆጠራ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም ተናግረዋል፡፡
የህንጻ ስር ፓርኪንግ አገልግሎት ለመስጠት መስፈርቱን የሚያሟሉ ባለንብረቶች በጊዜ ገደብ ወደ ስራ እንዲገቡ እየተደረገ እንደሆነና ለአገልግሎቱ ክፍት ባለደረጉ ባለህንጻዎችም ደንቡን መሰረት በማድረግ በክትትል እና ፍተሻ በገንዘብ ቅጣት እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ አቶ ቢኒያም አስረድተዋል፡፡
የህንጻ ስር ፓርኪንግ ቦታዎች ለታለመላቸዉ አላማ ብቻ መዋላቸዉ መንገድ ላይ የሚቆመዉን ተሽከርካሪ የሚቀንስ በመሆኑ የትራፊክ ፍሰቱም በዛዉ ልክ እንደሚያሳልጥ የተናገሩት አቶ ቢኒያም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በአግባቡ አገልግሎት ለሚሰጡ የህንጻ ባለንብረቶች የብቃት ማረጋገጫ ፍቃድ እየሰጠ እንደሚገኝም ጠቁመዋል፡፡
በባላስጣን መስሪያ ቤቱ የፓርኪንግ ቦታዎችን አቅርቦት ከመጨመረ በተጋዳኝ በዳታ ሲስተም ማስተሳሰር ጊዜዉ የሚጠይቀዉ ጉዳይ በመሆኑ አዲስ የፓርኪንግ መቆጣጠሪያ ሲስተምን ስራ በማስጀመር ተገልጋዩ ህብረተሰብ በቀላሉ ፓርኪንግ አገልግሎትን የሚያገኝበት ሁኔታ እየተሰራበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡
እንደ አቶ ቢኒያም ገለጻ በሁለተኛዉ ዙር የመንገድ ኮሪደር መሰረተልማትም የተሸከርካሪ ማቆሚያ መሰረተልማትን ለመጨመር በቅንጅት እየሰተራ እንደሆነ እና ወደፊት ተሽከርካሪዎች ከመንገድ ዉጭ በተዘጋጀላቸዉ ቦታ እንዲቆሙና  ዋና ዋና መንገዶች ለትራፊክ እንቅስቃሴ ብቻ እንዲውሉ ይደረጋል፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

23 Jan, 08:21


🎯ይህ ከታች በምስሉ ላይ የምትመለከቱት አደጋ ሲኤምሲ መንገድ (ከኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩንቨርሲቲ)ፊት ለፊት የደረሰ ነው፡፡
🚦በዘርፉ የተጠኑ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በከተማችን በትራፊክ አደጋ ከሚሞተው ከ80% በላይ እግረኛው ሲሆን ለዚሁም እንደምክንያት የሚቀርበው ከ85% በላይ በአሽከርካሪው ስህተት ነው፡፡
💔በተለይም እግረኞች በሚሻገሩበት ዜብራ ላይ ህይወቱን የሚያጣው እና አካሉ የሚጎድልበት እግረኛ እጅግ የበዛ ነው፡፡
⚠️በመሆኑም አሽርካሪዎች በየትኛውም ቦታ እና ሁኔታ ለእግረኞች ቅድሚያ በመስጠት ከአደጋ እንዲጠብቋቸው ከፍተኛ ሃላፊነት አለባችሁ!

TMA (Traffic Management Authority)

22 Jan, 08:24


ውድ የከተማችን መንገድ ተጠቃሚ አሽርካሪዎች እና እግረኞች እንደ ሁልጊዜው ሁሉ ማንኛውንም ሃሳብ፣ አስተያየት እና ጥቆማዎቻችሁን በጽሁፍ፣ በፎቶ፣ በድምጽ፣ በቪዲዮ እያደረጋችሁ ከታች በፎቶ ያስቀመጥንላችሁን ኪው አር ኮድ ስካን በማድረግ መላከ ትችላላችሁ፡፡
በተጨማሪ ከ22 ጎላጉል አደባባይ ወደ መገናኛ በሚወሰስደው መንገድ መክሊት ህንፃ በዋና ቢሯችንና በ11ዱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቻችን በአካል በመምጣት የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት እደምትችሉ መጠቆም እንፈልጋልን፡፡
በከተማዋ የትራፊክ ግጭት እንዳይደርስና ፍሰቱም ሰላማዊ እንዲሆን ተቋሙ የሚያደርገውን ጥረት አግዙ፡፡
እንደዚሁም ዘመኑ የዲጂታል ሚዲያ ነውና የባለስልጣን መ/ቤቱን ፌስቡክ እና ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን ከታች ያለውን ኪው አር ኮድ ስካን በማድረግ ሁሉንም የማህበራዊ አድራሻዎቻችን በመወዳጀት ተከተሉን፡፡ ለወዳጅ ዘመዶቻችሁም በማጋራት እና በመጋበዝ በየእለቱ በተቋሙም ሆነ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ የሚተላለፉ የዜና ዘገባዎችን፣ አጫጭር ትምህርታዊ መልእከቶችን፣ የብሮድካስት ፕሮግራሞችን፣ ማስታወቂያዎችን ወዘተ… ይከታተሉ፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

22 Jan, 07:37


ጉግል ማፕን በመጠቀም ግዜዎን ይቆጥቡ!
በእጅዎ በያዙት ስልክ በጉግል ማፕ በመመራት በአጭር ጊዜ በሚያደርስዎት መንገድ በትራፊክ መጨናነቅ ሳይጉላሉ የፈለጉበት ቦታ መድረስ ይችላሉ!
****************
አጠቃቀሙም፡-
ለአጠቃቀም የሚመችዎትን ማንኛውንም browser መክፈት፣
የከፈቱት Browser ላይ ጉግል ካርታ (Google Maps) ብሎ በመፃፍ ፈልግ የሚለውን መጫን፣
የመፈለጊያ አውታሩ ላይ በመጀመርያ የሚያገኙትን የጉግል ካርታ (Google Maps) የሚለውን ሊንክ መጫን፣
የሚሄዱበትን ቦታ በመፃፍ ፈልግ የሚለውን መጫን፣
ሂድ (start) የሚለውን በመጫን በማፑ በመመራት የሚሄዱበት ቦታ መድረስ ይችላሉ፣
በአማራጭ የጉግል ማፕ አፕልኬሽን (Google map application) በስልክዎ ላይ በመጫን መጠቀም ይችላሉ፣
በየቀኑ የሚመላለሱበት የስራ ቦታ ወይም የድርጅትዎ ቦታን እና መኖሪያ ቦታን በአፕልኬሽኑ ላይ በመጫን በየቀኑ ቦታዎቹን መፈለግ ሳይጠበቅብዎት በቀላሉ መጠቀም ይችላሉ፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

22 Jan, 05:54


አሽከርካሪዎች ከቤታችን ስንወጣ የጎግል ማፕ (Google Map) መተግበሪያ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በከተማዋ መንገዶች ላይ ያለውን የትራፊክ ፍሰት ሁኔታን ማወቅ ባህላችን እናድርግ!
መልካም ቀን!

TMA (Traffic Management Authority)

21 Jan, 12:00


ማስታወቂያ፡-

TMA (Traffic Management Authority)

17 Jan, 14:02


የልደታ ርንጫፍ ጽ/ቤት በዕቅድ አፈጻጸም ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ
• ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ስድስት ወር 19,143 ደንብ ተላላፊ አሽከርካሪዎች ላይ የጥፋት ቅጣት መጣሉን ገልጿል
(ት/ማ/ባ ጥር 09/2017 ዓ.ም)፡- የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የልደታ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር በዛሬው ዕለት ተወያይቷል፡፡
በጽ/ቤት የመንገድ ደህንነት ግንዛቤና አቅም ግንባታ ቡድን መሪ አቶ ነህምያ የጽ/ቤቱን ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ቁልፍ ተግባራትና ዐበይት ተግባራት አፈጻጸም ፣ ዓላማ፣ የሪፎርም መሳሪያዎችን ቅንጅታዊ ትግበራ ውጤታማ በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍና እና መልካም አስተዳደርን በማስፈን የተሻለ አፈጻጸም እንዲኖር ማድረግ እንደሆነ ገልጸዋል:፤
አያይአውም በስድስት ወር ውስጥ በመንገድ ትራንስፖርት መቆጣጠሪያ ደንብ ቁጥር 395/2009 መሠረት በዲስፒሊን፣ ቦሎ ባለመለጠፍ እና አለማደስ፣ ትርፍ ሰው በመጫን በአጠቃላይ 19,143 ደንብ ተላላፊ አሽከርካሪዎች ላይ የጥፋት ቅጣት መጣሉን አቶ ንህምያ አብራርተዋል፡፡
በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሥራ አፈጻጸም የተስተዋሉ ጠንካራ ጎኖች፣ መሻሻል የሚገባቸው እና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች በሪፖርቱ የተመላከቱ ሲሆን ሥራዎችን በተቀመጠላቸው ጊዜ ማከናወን መቻሉ እንዲሁም የሠራተኛው የሥራ ተነሳሽነት በጥንካሬ የቀረቡ ናቸው፡፡
በመቀጠልም በውይይት መርሓ ግብሩ ላይ በደንብ ቁጥር 557/2016 ላይ የግንዛቤ ማሳደጊያ ሰነድ ያቀረቡት የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የትራፊክ ቁጥጥርና ኩነት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አያለው ኢቲሳ በደንቡ ላይ የተቀመጠው በአሽከርካሪዎች የሚፈጸሙ ጥፋቶች እና የጥፋቶቹ እርከኖች፣ በጥፋቶቹ የሚቆጠር የቅጣት ነጥብ እና የቅጣት መጠን እና የሚወሰዱ ርምጃዎች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በቀረቡት ሰነዶች ላይ ከባለድርሻ አካላት የተለያዩ አስተያየቶችና ጥያቄዎች ተነሥተው ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን የልደታ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ተስፋዬ እንደገለፁት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በ45 ፐርሰንት የሰው ኃይል ብዙ ሥራዎችን መሥራቱ የሚበረታታ ሲሆን በቀጣይ ጊዜያት ሥራዎችን አጠናክረን እንሠራለን ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የተሻለ አፈጻጸም ላላቸው ባለድርሻ አካላትና ሠራተኞች የምስክር ወረቀት በመስጠት የዕውቅና መርሓ ግብር አካሂዷል፡፡
በኤልያስ ተስፋዬ
ፎቶ በአማረ ጠገናው

TMA (Traffic Management Authority)

17 Jan, 13:09


ከጥር 10 እስከ ጥር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ ጃን ሜዳ እና አቃቂ ቃሊቲ ታቦት ማደሪያ በሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል ምክንያት የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ስለሚሆኑ አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡
***
የ2017 ዓ/ም የከተራና የጥምቀት በዓል ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበር በጥምር የፀጥታ አካላቱ ቅድመ ዝግጅት ተጠናቆ ወደ ስራ መገባቱ ይታወቃል። በዓሉ በሚከበርባቸው ቦታዎች ሁሉ ከአካባቢው ነባራዊ ሁኔታ ጋር የተጣጣመ የስምሪት አቅጣጫን በመከተል ፀጥታ የማስከበር ተግባሩ የሚከናወን ሲሆን ከዚህም ጋር ተያይዞ ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ በ11ዱም ክ/ከተሞች ጥምቀተ ባህር ባሉባቸው ቦታዎች ሁሉ በ500 ሜትር ክልል ውስጥ ታቦታት ሲወጡና ሲገቡ እንዲሁም በሚሄዱባቸው መንገዶች ለአጭር ጊዜም ይሁን ለረዥም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አስታውቋል።
እንዲሁም ከጥር 10 እስከ ጥር 12 ቀን 2017 ዓ/ም ድረስ በጃን ሜዳ እና አቃቂ ቃሊቲ ታቦት ማደሪያ በሚከበረው የከተራና የጥምቀት በዓል ምክንያት በአካባቢው የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር፦
👉 ከ6 ኪሎ አደባባይ - ምኒልክ ሆስፒታል
👉 ከምኒልክ ሆስፒታል - መከላከያ 3ኛ ሻለቃ አደባባይ
👉 ከ3ኛ ሻለቃ አደባባይ - 6 ኪሎ አደባባይ እንዲሁም አቃቂ ቃሊቲ አካባቢ
👉 ከዋልያ ቢራ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል
👉 ከአቃቂ ዋናው መንገድ - ጥሩነሽ ቤይጂንግ ሆስፒታል
👉 ከ08 - አቃቂ ድልድይ ድረስ ከጥር 10 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ መንገዱ ለተሽከርካሪዎች ዝግ ስለሚሆን አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን መጠቀም እንደሚገባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን እያስተላለፈ በዓሉ የሠላምና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን ይገልጻል።

TMA (Traffic Management Authority)

16 Jan, 11:52


የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስጣን የከተማዋን የትራፊክ ፍሰት ለማሳለጥና ደህንነቱም የተጠበቀ እንዲሁም ተቀባይት ያለው የትራፊክ እቅስቃሴ ለማስፈን በሚያችል መልኩ የመንገድ ቀለም ቅብ ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
የመንገድ ተጠቃሚዎች በተለይም አሽርካሪዎች በህዝብ እና የመንግስት ሃብት ፈሶባቸው የተቀቡ ቀለሞች/ሌኑን ጠብቀው በማሽርካር ረዥም ግዜ እንዲያገልግሉ በማድረግ ራሳቸውንም ከቅጣት እዲጠብቁ ከማድረግ ባለፈ ከእግረኛ መሻገሪያ ቀደም ተብሎ የተሰመሩ መስመሮች ላይ በመቆም እግረኛን ማሻገር ልማድ እንዲያደርጉ ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ ያሳስባል፡፡
ለሰላማዊ እና ደህንነቱ ለተጠበቀ የትራፊክ እንቅስቃሴ በጋራ እንስራ!

TMA (Traffic Management Authority)

16 Jan, 08:25


የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የመንገድ ደህንነት ምህንድስና ዳይሬክቶሬት በከተማዋ የሚያከናውነው የመንገድ ቀለም ቅብ ስራና የምልክትና ማመልከቻ ተከላ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው...

TMA (Traffic Management Authority)

03 Jan, 15:50


https://www.facebook.com/aartmatmc/videos/1328365128596647/

TMA (Traffic Management Authority)

03 Jan, 15:49


“ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለገና በዓል በሠላም አደረሳችሁ”

~ የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚደቅሳ የመልካም ምኞት መግለጫ

TMA (Traffic Management Authority)

02 Jan, 14:57


ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በቅርቡ ተግባር ላይ በሚያውለው በተሻሻለው የመንገድ ትራፊክ መቆጣጠርያ ደንብ ,እና
ዛሬ ይፋ ባደረገው አውቶማቲክ የትራፊክ መቆጣጠርያ ሲስተም ዙርያ የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር. ኢ/ር ኤልያስ ዘርጋ ዛሬ ምሽት ከ 1:00 እስከ 3 :00 በኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የካሪቡ አውቶሞቲቭ ፕሮግራም ላይ እንግዳ ሆነው ይቆያሉ:: እንድትከታተሉት ጋብዘናል!

TMA (Traffic Management Authority)

20 Dec, 07:28


በፓርኪንግ አገልግሎት ለተደራጁ አካላት ስልጠና ተሰጠ
*************
(ታህሳስ 11/2017 ዓ.ም)፡- የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የተሽከርካሪ ማቆሚያ ቦታዎች ላይ የፓርኪንግ አገልግሎት በመስጠት ላይ ለተደራጁና ከ11ዱም ክፍለ ከተሞች ለተውጣጡ 248 ሴቶችና ወጣቶች በአገልግሎት አሰጣጥ እና በመልካም ስነምግባር ዙሪያ በትናንትናው እለት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
በተቋሙ የፓርኪንግ፣ የመንገድ ትራፊክ መሰረተ-ልማት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ቢኒያም ጌታቸው በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት በከተማዋ የመጀመሪያ ዙር በተካሄደ የኮሪደር ልማቱ ካስገኛቸው ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች መካከል ለተሽከርካሪዎች የመቆሚያ ቦታ ግንባታና በአገልግሎት መስጫው ለሚደራጁ ሴቶችና ወጣቶች ደግሞ የስራ እድል መፍጠር ይገኝበታል፡፡
በዚህም መሰረት ስልጠናው ያስፈለገበት ዋንኛው ምክንያት በፓርኪንግ አገልግሎት ለሚሰጡ አካላት በስራቸው ወቅት ደንብ ቁጥር 04/2012፣ ፋይናነስ አያያዝና አመዘጋገብ ላይ የተመለከተውን መረጃ አንዲያውቁና በመልካም ስነ-ምግባር ታንጸው አገልግሎቱን እንዲሰጡ ለማድረግ እንደሆነ አቶ ቢኒያም ተናግረዋል፡፡
ባለሰልጣን መ/ቤቱ የፓርኪንግ አገልግሎት አቅርቦት ለመጨመር እየሰራ ባለበት በአሁኑ ወቅት በመጀመሪያው ዙር የመንገድ ኮሪደር መሰረተ ልማት 44 የመኪና ማቆሚያ ቦታዎች መገንባታቸው ለተቋሙ ትልቅ እገዛ እንደሆነ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፤

በመኳንንት ምናሴ
ፎቶ በአማረ ጠገናው

TMA (Traffic Management Authority)

18 Dec, 13:40


በስታንዳርድ መዝገባና መልካም አስተዳደር ዙሪያ ክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና ተሰጠ
******************
(ታህሳስ 9/2017 ዓ.ም):- በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በስታንዳርድ ምዝገባና መልካም አስተዳርን የተመለከተ የክህሎት ማሳደጊያ ስልጠና ለፈጻሚ ባለሙያዎች ሰጠ፡፡
የስልጠናው ዋና ዓላማ በጽ/ቤቱ የሚገኙ ባሙያዎች በየደረጃው ያሉ ፈጻሚ አካላትን የስታንዳርድ አመዘጋገብና ንጽጽር ጽንስ ሃሳብ በማስጨበጥ አመራሩና ፈፃሚው መሃል ለአፈጻጸም ክትትል፤ ግምገማና ምዘና ስርዓት መዘርጋት የሚያስችል ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ነዉ፡፡
በእለቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ክትትል ድጋፍና ምዘና ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት ብሩክ በለጠ ለፈጻሚ ባለሙያዎች ሰነድ አቅርበዋል፡፡ የአገልግሎት አሰጣጥ ሳይንሳዊ የምዝገባና የንጽጽር ሂደት/ስሌት እንዲሁም የስታንዳርድ አፈጻጸም ንጽጽር ውጤት አሰራር የሚሉ ጉዳዮችን አቶ ብሩክ በሰነዳቸው ከዳሰሷቸው አንኳር ነጥቦች ውስጥ የሚገኙ ናቸው፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ የመንገድ ደህንነት ግንዛቤና ደንብ ማስከበር ዳይሬክቶርት ዳይሬክተር ገዛሄኝ ታምሩ የመልካም አስተዳደር ምንነት፣ የትግበራ ፍሬም ወርክ፣ የመልካም አስተዳደር መርሆዎች፣ ለቅሬታና አቤቱታ ምክንያት እና መንስኤዎች በሚሉ ጭብጦች ዙሪያ ሰነድ ለሰራተኛው አቅርበዋል፡፡
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አኪያጅ ወ/ሮ ሕይወት ታደሰ እንዳሉት በስታንዳርድ አመዘጋገብና መልካም አስተዳደር ላይ የተሰጡት የግንዛቤ እና ክህሎት ማሳደጊያ ስልጠናዎች ለሰራተኛው በቀጣይ የሚተገብራቸውን ተግባራት በጊዜ በጥራትና በመጠን ስታንዳርዱ መሰረት መዝግቦ እንዲይዝና ለሚመለከተው አካል በሪፖርት እንዲያቀርብ ስለሚረዳው ጠቃሚ እንደሆነው ሁሉ በመልካም አስተዳደር ላይ የተሰጠውም ስልጠና እንደዚሁም ለፈፃሚ ባለሙያው አወንታዊ ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል፡፡ በስልጠናው የተሳተፉት ሰራተኞች መሰል በመርሀ-ግብሮች የሰራተኛውን አቅም ስለሚያጎለብቱና ለውጤትም ስለሚያበቁ ጥሩ እና ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋ፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

05 Dec, 07:04


በከተማችን ከ80% በላይ የትራፊክ አደጋ የሚደርሰው በእግረኛው ላይ ሲሆን ለአደጋውም እንደመንሲኤነት የሚጠቀሰው በአሽከርካሪው ከፍጥነት ወሰን በላይ ማሽርካር እና ለእግረኞች ቅድሚያ አለመስጠት በተለይም በመሻገሪያዎች አከባቢ እንደሆነ በዘርፉ የተጠኑ ጥናቶች ያመላክታሉ፡፡
አዎ! አሽከርካሪዎች ዘወትር ለእግረኛው ቅድሚያ ይስጡ፤ በተለይም ዜብራ አከባቢ!

TMA (Traffic Management Authority)

04 Dec, 11:40


የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አማረ ታረቀኝ በአርቲስ ቲቪ ከካሪቡ አውቶሞቲቭ ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ

TMA (Traffic Management Authority)

04 Dec, 09:10


የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አማረ ታረቀኝ በአርቲስ ቲቪ ያደረጉት ቃለ ምልልስ

TMA (Traffic Management Authority)

02 Dec, 07:01


ሁሉም የመዲናዋ የመንገድ ተጠቃሚ ማህበረሰብ የሚተላለፉ የመንገድ ደህንነት ትምህርቶችን በመተግበር የትራፊክ አደጋን ይከላከል፡፡
ከአሽከርካሪ ግጭት የጸዳ መልካም የስራ ሳምንት እንዲሆን የባለስልጣን መ/ቤቱ የመኛል

TMA (Traffic Management Authority)

27 Nov, 09:20


“ሐገራዊ መግባባት ለሕብረብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል የባለስጣን መ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች 19ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በደማቅ ስነስርዓት ሲያከብሩ

TMA (Traffic Management Authority)

27 Nov, 07:54


የባለስልጣን መ/ቤቱ አመራሮች፣ሰራተኞችና ባለድርሻ አካላት የዘንድሮዉን አለም አቀፍ የትራፊክ አደጋ ተጎጂዎችን ቀን በዚህ መልኩ አስበዉ ዉለዋል

TMA (Traffic Management Authority)

25 Nov, 09:38


“ሐገራዊ መግባባት ለብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል የባለስጣን መ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች 19ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀንን በደማቅ ስነስርዓት አከበሩ
*********************
(ህዳር 16/2016 ዓ.ም)፡- የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አመራሮችና ሰራተኞች “ሐገራዊ መግባባት ለብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል 19ኛውን የብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀንን በተለያዩ መረሃ-ግብሮች በዛሬው እለት አክበረዋል፡፡
አገራችን ኢትዮጵያ የብዙሃን መነሐሪያ፣ ውብ እና ሁላችንም ተፈቃቅረን የምንኖርባት የወል መሬታችን፤ አባቶቻችን በደም እና አጥንት አጽንተው ያቆዩልን አገራችን ነችና እያንዳንዳችን በመዋድድ፣ በአንድነትና በፍቅር ልንጠብቃት ይገባል ሲሉ የእለቱን መረሃ-ግብር አስመልክተው የመክፈቻ ንግግርና ማብራሪያ ያደረጉት የባለስልጣን መስሪ ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚደቅሳ ናቸው፡፡
ይሁን እንጂ ትናንት ይዘን የመጣነው የተዛቡ ትርክቶች ዛሬም በመካከላችን ሰላምና ብልጽግናችን በሚፈለገው ልክ እንዳናረጋግጥ ወደኋላ እያስቀሩን ነው ያሉት አቶ ክበበው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት ሲል መንግስት በተጠናከረ ሁኔታ እየሰራ እንደሚገብና ዜጎችም ለውጤታማነቱ መደገፍ አንዳለባቸው አብራርተዋል፡፡
19ኛውን የብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህሕቦችን ቀንን ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር ታጅቦ የተጀመረው በዚሁ ፕሮግራም በፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ኢትዮጵያ ፌዴሬሽን ም/ቤት የተዘጋጀውን መነሻ ጹሁፍ በባለስልጣን መ/ቤቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ክትትል ድጋፍና ምዘና ዳይሬክተር አቶ ጎይቶም አስፋው ለአመራሩና ሰራተኛው አቅርበዋል፡፡
ፌዴራሊዝምና ፌዴራል ስርዓቱን በትክክለኛ እሳቤ መገንባት፣ ህገመንግስታዊነትን ማዳበር፣ የፌዴራል ስርዓቱን ለመገንባት መሰረት የሆኑ ጉዳዮችን ለአገራዊ መግባባት እና ግንባታ ልንጠቀምባቸው ይገባል የሚሉ ነጥቦች በመነሻ ጽሁፉ ውስጥ የተካተቱ አንኳር ጉዳዮች ናቸው፡፡
በቀረበው መነሻ ሰነድ ዙሪያ ሃሳብ አስተያየትና ጥያቄዎች ከተሳታፊዎች የተነሱ ሲሆን የባለሰልጣን መስሪያ ቤቱ የበላይ አመራሮች መሪነት ውይይትና ምላሽ ተደርጎበት ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡
ሳምንቱ በገባ የመጀመሪያው ቀን ዘወትር ሰኞ እለት እየተከበረ የሚገኘው የሰራተኛው የአብሮነት ቀንም የእለቱን ፕሮግራም አስታኮ ተከናውኖ ውሏል፡፡

በመኳንንት ምናሴ
ፎቶ በአማረ ጠገናው

TMA (Traffic Management Authority)

25 Nov, 09:10


📌

TMA (Traffic Management Authority)

20 Nov, 10:43


ባለስልጣን መ/ቤቱ የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀም ተከትሎ አጠቃላይ የተቋሙን የሪፎርም ሁኔታ ከገመገመ በኋላ ማስተካከያዎችን አድርጓል
********************
(ት/ማ/ባ ህዳር 11/2017 ዓ.ም)፡- እደሚታወቀው መንግስት እንደ ሃገር ብሎም እንደ ከተማ አቀፍ መዋቅራዊ ለውጥ በማምጣት ለህዝባችን የሚመጥነውን ቀልጣፋና ተደራሽ አገልግሎት መስጠት እንዲያስችለው የተለያዩ የሪፎርም ስራዎችን እያካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ሪፎርም ከተካሄደባቸው የመዲናዋ ተቋማት ዉስጥ አንዱ ነው፡፡ ባለስልጣን መ/ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት በመገምገም ከማእከል እስከ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ስራዎች ያሉበትን የአፈጻጸም ደረጃ ከተቋሙ ራእይና ተልእኮ አንጻር በመቃኘት በጥልቀት ከገመገመ በኋላ በስራ ዉስጥ ያሉ ጥናካሬዎች እና ድክመቶችን ለይቷል፡፡
በተጨማሪ የተቋሙ ሪፎርም ያለበትን ደረጃ በዝርዝር መርምሮ በየደረጃዉ የተሰጡትን ግብረ-መልሶች ከግምት ውስጥ በማስገባት የተቋሙን ሪፎርም በተሻለ ሁኔታ ዉጤታማ ለማድረግ እንዲቻል የቅርንጫፍ አመራሮች እና ዳይሬክተሮች ላይ ማስተካከያ ተደርጓል፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

19 Nov, 10:13


📌

TMA (Traffic Management Authority)

16 Nov, 09:30


ዓለም አቀፍ የትራፊክ አደጋ ተጎጂዎች መታሰቢያ ቀንን ምክንያት በማድረግ የጎዳና ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ ተጀመረ
************************
(ት/ማ/ባ ህዳር 7/2017 ዓ.ም):- በዓለም ለ20ኛ በሃገራችንና በከተማችን ለ18ኛ ጊዜ ህዳር በገባ ከመጀመሪያዎቹ ቀናት ጀምሮ ለ1 ወር በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ታስቦ የሚውለው የትራፊክ አደጋ ተጎጂዎች ቀንን ምክንያት በማድረግ በጊዮርጊስ አደባባይና አከባቢው የጎዳና ላይ የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ ማስጨበጫ ንቅናቄ በዛሬው እለት ተጀምሯል፡፡
የመታሰቢያ ቀኑን ዓላማ የገለፁት እና በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ አማረ ታረቀኝ እንደተናገሩት ዛሬ በዓለም፣ በሀገር እና በከተማችን ደረጃ በሰዎች ስህተትና በሰው ሰራሽ ምክንያት የሚከሰተውን የመንገድ ትራፊክ አደጋን ልንከላከለው እንችላለን ካሉ በኋላ ቀኑን ስናስብ በአደጋው የተጎዱትን ወገኖቻችን ልናስብ፣ ልንደግፋቸውና ልንከባከባቸው ይገባልም ሲሉ በአደራ ጭምር ተናግረዋል ም/ዋና ዳይሬክተሩ፡፡
እንደ አቶ አማረ ገለጻ ሁሉም የመንገድ ተዋንያን መደጋገፍን መርህ በማድረግ የመንገድ ትራፊክን መከላከልና ማስቆም ይቻላል። በዚህ መርሓ ግብር የታደምን አካላት ቃል ገብተን ወደ ተግባር መለወጥ ይኖርብናል እንዲሁም የሃይማኖት አባቶች እና የሚዲያ አካላት በመንገድ ትራፊክ አደጋ ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ እንዲሠሩ መልዕክት በማስተላለፍ ንቅናቄውን አስጀምረውታል።
በእለቱ በመንገድ ደህንነት ግንዛቤ እና አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የተዘጋጁ በመንገድ ደህንነት ላይ ያተኮሩ የህትመት ውጤቶች ብሮሸር፣ በራሪ ወረቀት እንዲሁም መጽሄት በከተማዋ የመንገድ ተጠቃሚ ለሆኑት እግረኛና አሽከርካሪዎች ማሰራጨት የተቻለ ሲሆን በተጨማሪ በድምጽ-ማጉያ የተደገፈ ገጽ ለገጽ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ግንዛቤም ተሰጥቷል፡፡
በንቅናቄ መድረኩ ላይ የባለስልጣን መ/ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ስራ አስኪያጆች፣ የትራፊክ ፖሊስ አባላት፣ የደህንትና ደንብ አስከባሪ አካላት፣ የመንገድ ደህንነት ግንዛቤና ቁጥጥር ባለሙያዎች፣ በጎ ፍቃድ የትራፊክ አስተናባሪ ወጣቶች እንዲሁም ልዩ ልዩ የመዲናዋ የህብረተሰብ ክፍሎች በመረሃ-ግብሩ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
የተጎጂዎች መታሰቢያ መረሃ-ግብር ከዛሬ ህዳር 07/2017 ዓ.ም ጀምሮ በልዩ ልዩ ፕሮግራሞች ማለትም በቶክ ሾው፣ በፓነል ውይይት፣ በደም ልገሳ፣ በእግር ጉዞ እና ተጎጂዎችን በመደገፍ በማገዝና በመንከባከብ ለቀጣይ 23 ተከታታይ ቀናት እየተከበረ የሚቆይ ይሆናል፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

15 Nov, 13:14


ለሚዲያ ተቋማት
***********
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስጣን ዓለም አቀፍ የትራፊክ አደጋ ተጎጂዎች መታሰቢያ ቀንን በተለያዩ ሁነቶችና የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ለማክበር ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቋል፡፡
የተጎጂዎች መታሰቢያ ቀንን ምክንያት በማድረግ ከቅዳሜ ህዳር 7/2017 ዓ.ም እስከ 30/2017 ዓ.ም የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ የንቅናቄ ፕሮግራም የተያዘ ሲሆን ነገ ቅዳሜ 7/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ላይ የጎዳና ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ማስጀመሪያ መረሃ-ግብር ፒያሳ ሚኒሊክ አደባባይ ላይ ስለሚከናወን በቦታው ላይ በመገኘት ሁነቱን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንድታደርጉልን የተለመደ ትብራችሁን እንጠይቃለን፡፡

TMA (Traffic Management Authority)

02 Nov, 18:39


ባለስልጣን መ/ቤቱ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የስራ አፈፃፀምን የተመለከተ ግምገማዊ ውይይት አደረገ
*****
(ት/ማ/ባ ጥቅምት 23/2017 ዓ.ም)፡- የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በከተማዋ ሰላማዊና ተቀባይነት ያለው የትራፊክ እንቅስቃሴን ለማረጋገጥ በሚደረገው ሂደት በ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈፃፀም ግምገማ እና የቀጣይ ሩብ ዓመት የትኩረት አቅጣጫ ላይ በዛሬው ዕለት ተወያይቷል፡፡

በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዝግጅት ምዕራፍ በመሆኑ በሁሉም ዘርፍ ለሚከናወኑ ስራዎች አስፈላጊ የሆኑ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እና የሰነዶች ዝግጅት ከመጠናቀቁም በላይ ወደ ትግበራ ስለ መገባቱ የእቅድና በጀት ዳይሬከቶሬት ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ተሬሳ የተቋሙን የ3 ወራት የእቅድ አፈፃጸም ሪፖርት ሲያቀርቡ ገልጸዋል፡፡

በሩብ ዓመቱ ከተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት መካከል እግረኞች እና አሽከርካሪዎችን መሠረት ያደረጉ የምህንድስና ዘርፍ ማሻሻያዎች፣ በግንዛቤ የተደገፈ የቁጥጥር ስራዎች እንዲሁም የፓርኪንግ አገልግሎት አሰጣጥ እና አስተዳደር ስራዎች እንደሚገኙበት ዳይሬክተሩ አብራርተዋል:;

አያይዘውም በስራው ወቅት ያጋጠሙ ችግሮች፣ የተወሰዱ እርምጃዎች፣ እና በቀጣይ ሊስተካከሉ የሚገቡ ነጥቦችንም አንስተዋል፡፡

እንዲሁም በሩብ ዓመቱ የዋናው መ/ቤቱንና የ11ዱምን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እቅድ አፈፃፀምን የተመለከተ ክትትልና ድጋፍ ሲያደርግ የቆየው ኮሚቴ በበላይነት ሲመሩ የነበሩት አቶ ደረጄ ወርቁ ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን የውስጥ ኦዲት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰርኬ የኦዲት ምርመራ ግኝቶችና የአሰራር ግድፈቶች እንዲሁም በቀጣይ ማስተካከያ ሊደረግባቸው የሚገቡ ጉዳዮችን ያመላከተ ሪፖርት አቅርበዋል፡፡

በቀረቡት ሶስቱ ሰነዶች፣ በስራ ወቅት በነበሩ የግበዓት እጥረቶችና ተግዳሮቶች፣ በተወሰዱ የመፍትሄ መንገዶች እንዲሁም በቀጣይ ሊተገበሩ በሚገቡ ጉዳዮች እና መፍትሄዎች ላይ የማናጅመንት አባላቱ ሃሳብ፣ አስተያየት እና ጥያቄዎችን አንስተው በስፋት ተወያይተዋል፡፡

በመጨረሻም የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ክበበው ሚደቅሳ የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት አፈፃፀም አበረታች እንደነበረ እና ለቀጣይ የስራ ጊዜያትም ስንቅ በመሆኑ ለውጤቱ አስተዋጽኦ ላደረጉ የተቋሙ ሰራተኞችና አመራሮች ምስጋና አቅርበዋል:;

በተለይም በጥንካሬ የሚወሰዱት እቅድን በጠራ መልኩ እንዲታቀድ ጥረት መደረጉ; ከባለድርሻ አካት ጋር የተደረጉ የትስስር ሰነዶችና ውይይቶች፣ ለባለሙያዎች አቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎች መሰጠቱ እና የክረምት የማህበራዊ አገልግሎት ስራዎቾ ተጠቃሽ እንደሆኑ ዋና ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡

ይሁን እንጂ እንደ ተቋም ጥሩ አፈፃፀሞች እና ስኬቶች አጠናክሮ በመያዝ በዝግጅት ምእራፍ የታዪ ክፍተቶች እና ጉድለቶችንም በማስተካከል በቀጣይ ሩብ ዓመታት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባ አቅጣጫ አስቀምጠዋል::

በግምገማዊ ውይይቱ ላይ የባለስልጣን መ/ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጆች፣ ዳይሬክተሮች ተገኝተዋል፡፡

በመኴንንት ምናሴ
ፎቶ በአማረ ጠገናው

TMA (Traffic Management Authority)

31 Oct, 11:53


https://www.facebook.com/aartmatmc/videos/514549674785316/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

TMA (Traffic Management Authority)

30 Oct, 17:19


https://www.facebook.com/100064830633094/posts/1003557745148571/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

TMA (Traffic Management Authority)

28 Oct, 13:34


የመንገድ ደህንነት ጥንቃቄ መልእክት ለአሽከርካሪዎቻችን‼️

TMA (Traffic Management Authority)

28 Oct, 12:42


የባለስልጣን መ/ቤቱ ደጋፊ የሥራ ሂደቶች በአንደኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ላይ ተወያዩ
********************
(ት/ማ/ባ ጥቅምት 18/2017 ዓ.ም ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን ደጋፊ የሥራ ሂደቶች በ2017 በጀት ዓመት የአንደኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ላይ በዛሬው እለት ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የሥራ ክፍሎች የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱ ላይም የባለሙያ ዕቅድ ምን ደረጃ ላይ እንዳለ፣ አቻ ፎረም ያለበት ደረጃ፣ ከፕሮሰስ ካውንስል የወረዱ የሥራ አቅጣጫዎች ምን ደረጃ ላይ እንዳሉ እንዲሁም በሥራ አፈጻጸም ወቅት የተስተዋሉ ጥንካሬዎችና ክፍተቶች ቀርበዋል፡፡
አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸሙ በጥሩ ደረጃ ላይ ቢገኝም በአንዳንድ የሥራ ክፍሎች እቅድን በመዘንጋት በደራሽ ስራ የመጠመድ ሁኔታ አንዳለና መስተካከል አንደሚገባው በውይይቱ ላይ በአጽንኦት ተገልጽዋል፡፡
በቀረቡት ሪፖርቶች ላይም ከውይይቱ ተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች መልስ የተሰጠ ሲሆን የባልስልጣን መ/ቤቱ አማካሪ አቶ ዓለምሰገድ ዘውዴ እንዳሳሰቡት የበጀት ዓመቱ ዕቅድ ታቅዶ ወደ ሥራ እንደተገባ ጦቅመው ዕቅዶች ተናባቢ ሊሆኑ ይገባል፡፡
አቶ ዓለምሰገድ አክለውም እያንዳንዱ ባለሙያ ዕቅድ ሊኖረው እንደሚገባና አቻ ፎረምም በተቀመጠለት የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በቋሚነት እና ችግር ፈቺ በሆነ መንገድ መካሄድ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡
በመጨረሻም የሥራ ክፍሎች በውይይቱ በተነሱ ጉዳዮች እና አሠራሮች ላይ የጋራ አቋም ይዘው ውይይቱን አጠናቀዋል፡፡
በኤልያስ ተስፋዬ

TMA (Traffic Management Authority)

28 Oct, 07:13


ከትራፊክ አደጋ የፀዳ መልካም የስራ ሳምንት ለከተማችን የመንገድ ተጠቃሚዎች እንመኛን!