Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን) @getu_temesgen365 Channel on Telegram

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

@getu_temesgen365


Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን) (Amharic)

ጌጡ ተመስገን (Getu Temesgen) የጌጡ ተመስገን የቴሌግራም ክፍል ለማንበብ እና በመሀልዋል የሚገኙበት አገሮችን የሚያስተምሩ እና ሥራታዊ መረጃዎችን ለማድረግ የሚያሰናዱ ጥያቄዎች እና መልኩ ነው። የደረጃ እንቅስቃሴዎችን እና ከተለያዩ ግለቦች ጋር የሚበልጡበት የቴሌግራም ክፍል እናመሀልዋል ግምትን እና ተመልከቱን አገስቦ እናልካለን። Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን) ተብሎ ይህ ማህበረሰብን ያስተምርባችሁ ይውላል!

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

04 Jan, 00:05


በአፋር ክልል፣ ሳጋንቶ ቀበሌ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በበርካታ ሥፍራዎች ላይ ገንፍለው የውጡት ፍል ውሃዎች

#Ethiopia | በአፋር ክልል፣ ዱለሳ ወረዳ በተከሰት የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በበርካታ ሥፍራዎች ላይ ፍል ውሃዎች እየተፈጠሩ ይገኛሉ።

በወረዳው በሳጋንቶ ቀበሌ የደረሰውን የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ በስፍራው በአካል በመገኘት የመስክ ምልከታ ያደረገ የኢቢሲ ሪፖርተር በቀበሌው በበርካታ ሥፍራዎች ላይ ፍል ውሃዎች እየወጡ መሆኑን መታዘቡን ገልጿል።

በቀበሌው በተለይ በዶፈን ተራራ ላይ የመሬት መንቀጥቀጡ በመጠኑም በድግግሞሹም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሆኑን በዚህም ሳቢያ ተራራው እየተናደ እንደሆነ ገልጿል።

የመሬት መንቀጥቀጡ በፈጠረው ግፊት በቀበሌው እንፋሎት አዘል ፍል ውሃ እና ቅባት አዘል ጥቁር ውሃ ከመሬት እየፈለቀ መሆኑንም ጠቅሷልል።

በቀበሌው የሚኖረው አርብቶ አደር ማህበረሰብ ከሥፍራው ተነስቶ በሌሎች አካባቢዎች እንዲሰፍር እየተደረገ መሆኑን ገልጿል።

በመሬት መንቀጥቀጡ ሳቢያ በፈንታሌ እና በዶፈን ተራራ መካከል የተፈጠረው የመሬት ስንጥቅ ክፍተቱ እየጨመረ መሆኑንም አክሏል።

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

02 Jan, 15:54


የፈንታሌው የመሬት መንቀጥቀጥ ለኢትዮጵያ የማንቂያ ደወል ነው

#Ethiopia | ሰሞኑን በአፋር ክልል በፈንታሌ ተራራ እየተከሰተ ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ አዲስ አበባ ከተማ ድረስ ቢሰማም የከፋ ጉዳት ያደርሳል ተብሎ እንደማይጠበቅ በኢትዮጵያ ስፔስ ሳይንስ እና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የጂኦዴሲ እና ጂኦዳይናሚክስ መሪ ስራ አስፈፃሚ ናትናኤል አገኘሁ ገለጹ።

የመሬት መንቀጥቀጥ ምንም የማይተነበይ ወይም ተገማች ያልሆነ፣ በዋናነትም በተፈጥሮ ውስጣዊ ኃይል ምክንያት የሚፈጠር ክስተት መሆኑንም ነው አቶ ናትናኤል በተለይ ለኢቢሲ ዶት ስትሪም የገለፁት።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ዶ/ር ኤሊያስ ሌዊ እና በተቋሙ የዘርፉ ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አታላይ አየለ በበኩላቸው፥ የኤደን ባህረ ሰላጤ፤ የምስራቅ አፍሪካ እና የቀይ ባህር ስምጥ ሸለቆዎች በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ዓመታት ሲያደርጉት የነበረ መፈላቀቅ አሁንም የቀጠለ ተፈጥሯዊ ክስተት በመሆኑ የመሬት መንቀጥቀጥ እንዲከሰት ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።

ከአፋር አንስቶ በሀዋሳ፣ አርባ ምንጭ፣ ኤርትራ እስከ ቀይ ባሕር ያለው መስመር የታላቁ ስምጥ ሸለቆ መገኛ በመሆኑ በፈንታሌ አካባቢ እየተከሰተ ላለው የመሬት መንቀጥቀጥ አንዱ ምክንያት ነው ብለዋል።

የፈንታሌ የእሳተ ገሞራ ተራራ ቅልጥ አለት እስከ ዶፋን ድረስ 30 ኪሎ ሜትር ውስጥ ለውስጥ መሄዱን፤ የአካባቢው መሬት እስከ 33 ሴንቲ ሜትር በፊት ከነበረበት ወደ ላይ ከፍ ማለቱን ከሳተላይት የተገኘው መረጃ ያመለክታል ብለዋል።

የፈንታሌ ተራራ እስከ 13 ሴንቲ ሜትር ወደ ላይ መወጠሩን፤ ውጥረቱ ከላይ ያለውን ድንጋይ እንዲሰባበር ማድረጉን፤ ይህም ደካማ ቦታዎች ላይ መንሸራተትን መፍጠሩን፤ ድንጋይ ከድንጋይ ሲጋጭ የሚፈጠረው ንዝረትም ሞገዱ ተጎዞ ሰሞኑን እስከ አዲስ አበባ እየተሰማ መሆኑንም የተናገሩት።

ሰሞኑን በሬክተር ስኬል እስከ 5 የሚደርስ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን የተናገሩት ባለሙያዎቹ፤ ይህም በየቀኑ በተለያየ መጠን፣ በተደጋጋሚ እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ለመሬት፣ ለትምህርት ቤቶች፣ ለመኖሪያ ቤቶች፣ ለአንዳንድ ሕንጻዎች እና የአስፋልት መንገዶች መሰንጠቅ ምክንያት መሆኑን አንስተው፤ ክስተቱ የማንቂያ ደወል ነው ብለዋል።

ክስተቱ በፈንታሌ እሳተ ገሞራ አካባቢ ባሉ ነዋሪዎች ዘንድ ድንጋጤ መፍጠሩን ገልጸው፤ መጠኑ እየጨመረ ከሄደ በህብረተሰቡ ዘንድ የሚፈጠረውን ስጋት ለመቀነስ ተገቢ ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

የፈንታሌ አካባቢ ኢትዮጵያን ከጅቡቲ የሚያገናኘው መንገድና የባቡር መስመር የሚያልፉበት መሆኑን ጠቅሰው፤ ክስተቱን እንደማንቂያ ደወል በመውሰድ መንግሥት እንዲሁም የዘርፉ ምሁራንና ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሊሰጡት ይገባል ብለዋል።

የመሬት መንቀጥቀጥ እንዳይከሰት ማድረግ ባይቻልም አደጋው ቢፈጠር የሚያስከትለውን ጉዳት መቀነስ ይቻላል ያሉት ባለሙያዎቹ፤ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለህዝብ ወቅታዊ መረጃ ተደራሽ ለማድረግ በቅንጅት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመዋል።

በላሉ ኢታላ

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

22 Dec, 13:11


#Ethiopia | የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በአዲስ አበባ በነበራቸው ቆይታ በብሔራዊ ቤተመንግስት ያደረጉት ጉብኝት በፎቶ

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

18 Dec, 15:55


ቀላቲ ቢውቲ ድምጻዊ ቬሮኒካ አዳነን የብራንድ አምባሳደር ሆነች

#Ethiopia | ተወዳጅዋ ድምፃዊ ቬሮኒካ አዳነ ለቀላቲ ቢዉቲ ለቀጣይ ሁለት ዓመት የክብር አምባሳደር በመሆን ለቴሌቪዥን ፤ ለቢል ቦርድ እና ለማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ማስታወቂያዎች ለመስራት የብራንድ አምባሳደር በመሆን ተፈራርማለች።

በ2008 ዓ.ም በአቶ ሮቤል ቀላቴ የተመሠረተው ዋና መቀመጫውም በአዲስ አበባ ያደረገው ቀላቲ ቢዉቲ የተለያዩ የውበት መጠበቂያ ምርቶችን በኦን ላይን በማዘዝ ለደንበኞች ባሉበት ስፍራ ለማድረስ የተመሠረተ ተቋም ነው።

ተወዳጅዋ ድምፃዊ ቬሮኒካ ቀላቲ ቢውቲ ጋር ለመስራት እድሉን በማግኘቷ የተሰማትን ክብር በፊርማ መርሐግብሩ ላይ ገልጻለች።

ቀላቲ የኤርትራ ቋንቋ ሲሆን ትርጓሜው ስጦታ ማለት እንደሆነ እና በቀጣይ የተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎችን ለመስራት እንደታሰበ በመርሐግብሩ ላይ ተገልጿል።

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

08 Dec, 21:51


ለተፈጠረው የዜጎች ድንጋጤና መረበሽ ይቅርታ!

#Ethiopia | በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የጦር መሣሪያ ድምፅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ተሃድሶ ሥልጠና ማዕከላት በሚጓዙ የቀድሞ የኦነግ ታጣቂ ቡድን አባላት የተሰማ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አከባቢዎች የተሰማው የጦር መሣሪያ ድምፅ የመንግስትን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ወደ ተሃድሶ ሥልጠና ማዕከላት በሚጓዙ የቀድሞ የኦነግ ታጣቂ ቡድን አባላት የተሰማ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

መንግሥት በሀገሪቱ የተለያዩ አከባቢዎች ታጥቀው ለሚንቀሳቀሱ ቡድኖች ባቀረበው የሠላም ጥሪ መሠረት የኦነግ ታጣቂ ኃይል አባላት የሰላም ጥሪውን ተቀብለው በስፋት እየገቡ መሆኑ ይታወቃል።

የታጣቂ ቡድኑ አባላትን ወደ ተዘጋጀላቸው የተሃድሶ ስልጠና ማዕከላት የማጓጓዝ ስራ በስኬት እየተከናወነ ይገኛል።

በዚህ መሀል ታጣቂዎቹ አዲስ አበባ ከተማን አቋርጠው ወደ ስልጠና ማዕከላት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት እየጨፈሩና የደስታ ስሜት እያሰሙ ሲንቀሳቀሱ የተኩስ ድምጽ በማሰማታቸው በከተማው ነዋሪ ህዝብ ላይ ድንጋጤና መረበሽ ሊፈጠር መቻሉን ፖሊስ ገልጿል።

ለተፈጠረው የዜጎች ድንጋጤና መረበሽ ይቅርታ የጠየቀው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ በቀጣይ ተመሳሳይ ችግሮች እንዳይፈጠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄና የማስተካከያ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን አስታውቋል።

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

27 Nov, 21:40


በግለሰብ አካዉንት ገቢ ሲደረግ እንደነበር በኦዲት ተረጋገጠ

#Ethiopia  | ከፓስፖርት ቅጣት የተሰበሰበው ወደ 18 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ በግለሰብ አካዉንት ገቢ ሲደረግ እንደነበር በኦዲት ተረጋገጠ

ኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የፓስፖርት ቅጣት ክፍያን የመሰብሰብ ፍቃድ ሳይሰጠዉ የራሱን የመመሪያ ተመን በማዉጣት ሲሰራ እንደነበር ተገልጿል ።

ስልጣን ሳይሰጠዉ ከፓስፖርት የሚገኝ የቅጣት ገንዘብን እየሰበሰበ ይገኛል የተባለው አገልግሎቱ የገንዘብ ሚኒስትርን ሳያስፈቅድ የራሱን አካዉንት በመክፈት 17 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ገደማ ገቢ አድርጓል ተብሏል።

በራሱ የተመን መመሪያ ቅጣት ሲጥል የነበረዉ ተቋሙ ከ 1 ሺህ እስከ 1500 ብር እያስከፍል እንደነበር ካፒታል ከኦዲት ሪፖርቱ ተመልክቷል።

ይህ ገንዘብ ገቢ ሲደረግ የነበረዉ በግለሰቦች አካዉንት ተከፍቶ ነበር ያለዉ የፌዴራል ዋና ኦዲተር የተከፈተው " የባንክ አካዉንት ወደ ሰራተኞች መረዳጃ እድር ተቀይሯል ብሏል" ።

በዚህ ባልተፈቀደ አካዉንት ገቢ ተደርጓል ከተባለው ገንዘብ ዉስጥ 9 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሚሆነው ለትርፍ ሰዓት ክፍያ እና ለበዓል ወጪ መደረጉን እና 8 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ደግሞ በአካዉንቱ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።

የፌዴራል ዋና ኦዲተር በፓርላማ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ በቅጣት የተገኘው ገቢ ወደ መንግስት መተላለፍ የነበረበት ያለ ሲሆን ይህ ባለመሆኑ ህጉ መጣሱና ድርጊቱን የፈፀሙ አካላት ሊጠየቁ ይገባል ብሏል።

ይህ የተገለፀዉ ቋሚ ኮሚቴው የ2015 እና 2016 በጀት ዓመት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና ውጤታማነትን በተመለከተ የክዋኔ የኦዲት ሪፖርት ላይ ዉይይት ባደረገበት ወቀት ነዉ።

የኦዲት ግኝቱን በሚመለከት አሁን በአመራር ላይ የሚገኙ ኃላፊዎች አዲስ መሆናቸዉን ከመግለፅ ዉጪ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር ምላሽ ያልሰጠው ተቋሙ ያሉበትን የአሰራር ክፍተቶች ማሻሻል ማድረግ እንደሚገባው ማሳሰቢያ ተሰጥቶታል።

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

26 Nov, 20:56


❣️ "እያንዳንዱ ሕፃን የተስፋ ታሪክ ነው "
የሔዋን ፋውንዴሽን መስራች ሔዋን ቀለመወርቅ

#Ethiopia | ሔዋን ፋውንዴሽን "እያንዳንዱ ሕፃን የተስፋ ታሪክ ነው" በሚል መሪ ፅንሰ-ሐሳብ የሚመራ በተለያዩ ሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ችግሮች ወላጆቻቸውን ያጡ ከትምህርታቸውና ዕለት ተዕለት የሕይወት ጉዟቸው የተስተጓጎሉ የነገ ተስፋ የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎችን ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ እና እንደማንኛውም ቤተሰብ ያለው ልጅ ሆነው እንዲያድጉ የተስፋ ብርሐናቸው እንዳይጨልም ለማድረግ የተቋቋመ ሐገር-በቀል በጎ አድራጎት ተቋም ነው።

ተቋሙ በሁሉም አከባቢዎች ክፉኛ ለችግር የተጋለጡ ሕፃናት ከለላ እንዲያገኙ ከማድረግ ባሻገር የተስፋ ብርሐናቸው እንዳይጨልም በትምሕርት ገበታቸው ተገኝተው እንድማሩ በመደገፍ ለቁምነገር እንዲበቁ የማድረግ ዓላማን ያነገበ ነው።

የመጀመሪያውን የሕፃናት ማቆያ እና መማሪያ በአማራ ክልል ደብረብርሐን ከተማ ያስጀመሩት የሄዋን ፋውንዴሽን መስራች ሄዋን ቀለመወርቅ “በልጅነቴ ያየሁት ህልም አሁን እውን ሆኗል። እያንዳንዱ እርምጃ፣ እያንዳንዱ ፈተና፣ ሁሉም ወደዚህ መራኝ፤ ከህልም ወደ እውነታ፤ ዛሬ በልጅነት አድሜዬ ባሰብኩት ነገር ጫፍ ላይ ቆሜያለሁ። ይህንን አግኝቻለሁ እና እየጨመርኩ መሄዱን እቀጥላለሁ” ብለዋል።

የልጅነት ሕልሜን ወደ እውነት ቀይሬዋለሁ፤ በፅናት እና በእምነት ህልሞቼ እውን መሆናቸው አንደማይቀር የሚያሳይ ይህ ማረጋገጫ ነው የሉት ወ/ሮ ሄዋን ከልጅነት ምኞት ብልጭታ ጀምሮ እስከ የህይወት ዘመን ድል ዛሬ ህልሜን ወደ ህይወት ስላመጣሁ የልጅነት ህልሜ ተሳክቶ በማየቴ እየሱስ ክብሩን ይውሰድ ብለዋል።

ሄዋን ፋውንዴሽን ይሰፋል፤ ሌሎች ባለሐብቶችም በተለያዩ ምክንያቶች ወላጆቻቸውን ያጡ እና ለመማር አቅም የሌላቸው ሕፃናትን በመደገፍ የነገ ተስፋቸው ብሩሕ እንዲሆን ማሕበራዊ ግዳጃቸውን ቢወጡ የሚል መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

"እያንዳንዱ ሕፃን የተስፋ ታሪክ ነው"❣️

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

24 Nov, 22:35


"ቪኒ ጁኒየር የባሎንደኦር ሽልማቱን ተዘርፏል!"

#Ethiopia  | በ4 ሀገራት ጋዜጠኞች ምክንያት ቪኒ ጁኒየር ባሎንደኦሩን ተቀምቷል ሲሉ የማድሪዱ ፕሬዚዳንት ተናገሩ።

ፕሬዚዳንት ፍሎረንቲኖ ፔሬዝ በክለቡ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ረዥም ንግግር የዘንድሮው የወርቅ ኳስ ሽልማት ፍትሃዊ እንዳልሆነም ተናግረዋል።

የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር በምርጫው መካተቱ የምርጫ ሥርዓቱ ላይ ተጽእኖ እንደፈጠረም እምነት አለኝ ብለዋል።

ቪኒ ላለማሸነፉም የ4 ሀገራት መራጭ የስፖርት ጋዜጠኞችን ወቅሰዋል። የናሚቢያ፣ ኡጋንዳ፣ አልባኒያና ፊንላንድ ጋዜጠኞች ለቪኒ አንድም ድምጽ አልሰጡም ያሉት ፔሬዝ፤ የፊንላንዱ ጋዜጠኛ ራሱን ከምርጫ ውጭ ማድረጉ ከወቀሳ አትርፎታል ብለዋል።

የእነዚህ ሀገራት ጋዜጠኞች ድምጽ ቢሰጡት ኖሮ ቪኒ አሸናፊ ይሆን ነበር፤ አንዳቸውም ደግሞ አይታወቁም ብለው ወቅሰዋል።

ፍራንስ ፉትቦልና ሌ ኪፕ ከዩኤፋ ጋር መስራታቸውም ስሜት አይሰጥም ያሉት የማድሪዱ ፕሬዚዳንት፤ ባሎንደኦር በገለልተኛ አካላትና በሙያተኞች መመረጥ አለበት የሚል እምነት አላቸው።

መስፈርቶቹ ግልጽ ባይሆኑም የዘንድሮ አሸናፊዎች የማድሪድ ተጫዋቾች መሆን ነበረባቸው፤ ቪኒ ደግሞ ይገባው ነበር ብለዋል። ካልሆነ አንበላችን ዳኒ ካርቫሃል ወይም ጁድ ቤሊንግሃም ማሸነፍ ነበረባቸው ሲሉ አክለዋል።

የሲቲው አማካኝ ሮድሪ ከዓለም ምርጦች አንዱ መሆኑንና የባሎንደኦር ሽልማት የሚገባው መሆኑን ግልጽ ማድረግ እፈልጋለሁ ያሉት ፔሬዝ፤ የዘንድሮውን ግን ማሸነፍ አይገባውም ብለዋል።

ሮድሪ ባለፈው ዓመት ከክለቡ ጋር የሶስትዮሽ ዋንጫ ሲያነሳ፣ በቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ላይም ግብ ማስቆጠሩን፤ ነገር ግን በሽልማቱ ደረጃ እንኳን እንዳልገባ አስታውሰዋል። እናም አዘጋጆቹ ያለፈው ዓመት ስህተታቸውን ለመሸፈን ዘንድሮ አሸናፊ አድርገውታል፤ በነዚህና በሌሎች ምክንያቶች ቪኒ ሽልማቱን ተዘርፏል ብለዋል ፔሬዝ።

በፓሪሱ የሽልማት ሥነ-ሥርዓት አንድም የሪያል ማድሪድ ተጫዋችና አመራር አለመገኘቱ ይታወሳል።

በሁሴን ግዛው

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

23 Nov, 23:58


በአጼ ኃይለሥላሴ ዘመነ- መንግስት የተመዘገቡ እድገቶችና ያጋጠሟቸው ተግዳሮቶች

#Ethiopia  |  ቅዳሜ ህዳር 14 2017  ዓ.ም ከቀኑ 8:30 ጀምሮ  በብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና  ቤተ-መጽሀፍት  አዲሱ ህንጻ 9ኛ ፎቅ በተደረገው መርሀ ግብር ታላላቅ ሰዎች ታድመው ነበር::

የታሪክ አደራ ድርጅት ባዘጋጀው በዚህ የአርካይቭ ማእከል ምረቃ ሥነ-ሥርአት ላይ በአጼ ኃይለስላሴ ዘመነ- መንግስት የተመዘገቡ እድገቶችና ያጋጠሟቸው ተግዳሮቶች  በወቅቱ በነበሩ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ተዳሰዋል::

በዕለቱ ሀሣባቸውን ከሰነዘሩት መካከል  ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም  አገራቸውን ወደ ከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ለማድረስ የሄዱበትን ርቀት አብራርተው ገልፀዋል::

  በአጼ ኃይለስላሴ ዘመን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር በመሆን ከፍተኛ ኃላፊነት የነበራቸው አቶ በቀለ እንደሻው  የእርሳቸውን ዘመን ከኢኮኖሚ አንፃር በማየት ልዩ ሙያዊ ትንታኔ አቅርበዋል::

የብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጽሀፍት  ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር  አቶ ይኩኑአምላክ  መዝገቡ የአርካየቭ ማዕከሉ  በይፋ በመመረቁ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል::
የታሪክ አደራ ድርጅት የቦርድ ሊቀመንበር ወይዘሪት ሰብለ ነቢየልኡል የመዛግብት ማዕከሉ በታሪክ አደራ ድርጅት ስር ሆኖ ታሪክን ለወደፊቱ ትውልድ ተደራሽ  ማድረጉ ትልቅ ርካታ ሰጥቷቸዋል:: ይህም ዕውን እንዲሆን  የወመዘክር ዋና ዳይሬክተር መመስገን አለባቸው ብለዋል::

የታሪክ አደራ ድርጅት  የአርካይቭ ማዕከሉን በሚያስመርቅበት ዕለት  የድርጅቱ መሥራቾች እንዲሁም ደጋፊዎች የታደሙ ሲሆን  በዕለቱም በፊልም ባለሙያው የማነ ደምሴ የተዘጋጀ 20 ደቂቃ የጊዜ ፍጆታ ያለው ዘጋቢ ፊልምም ቀርቧል::

የታሪክ አደራ ድርጅት በ2014 የተቋቋመ ድርጅት ሲሆን  የተለያዩ መታሰቢያዎችን  የማቋቋምና የማስተዳደር ብሎም የማሻሻል ሥራዎችን የሚሠራ ነው፡፡ በተጨማሪም ታሪክ ላይ ትኩረቱን አድርጎ ጠቃሚ ተግባራትን የሚያከናውን ሲሆን  ነጻ የትምህርት እድሎችንም  ይሰጣል፡፡

የዚህ መርሀ ግብር ሁነት አዘጋጅ እንዲሁም አማካሪ ተወዳጅ ሚድያ እና ኮምዩኒኬሽን ሲሆን መድረኩን በመምራት ደግሞ ጋዜጠኛ እዝራ እጅጉ  ድርሻውን እንደተወጣ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

23 Nov, 22:22


75"' ማንችስተር ሲቲ 0 - 4 ቶተንሀም

#Ethiopia | ቶተንሀም ማንችስተር ሲቲ ላይሦሶስተኛ ግብ አስቆጥሯል

ማንቺስተር ሲቲ በሜዳው በቶተንሃም 4 ለ 0 ተሸነፈ

በ12ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ምሽት 2፡30 ላይ በተደረገ ጨዋታ ማንቺስተር ሲቲ በሜዳውና በደጋፊው ፊት በቶተንሃም ሆትስፐር 4 ለ 0 ተሸንፏል፡፡

በጨዋታው የቶተንሃም ሆትስፐርን የማሸነፊያ ግቦች ጀምስ ማዲሰን በ 13ኛው እና በ20ኛው ደቂቃ፣ ፔድሮ ፖሮው በ52ኛው ደቂቃ እንዲሁም ቤናን ጆንሰን በ94ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡

ማንቺስተር ሲቲ ይህን ጨዋታ መሸነፉን ተከትሎ በሁሉም ውድድር 5ኛ ተከታታይ ሽንፈቱ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

18 Nov, 22:46


❣️ እናታችንን አመሰገናት

#Ethiopia |እናቴ ለኔ ቋንቋዬ ናት። አፌንም የብዕሬንም ልሳን የፈታሁት በሷ ነው። አጠገቧ ተቀምጬ እሷ እንደ ቀልድ ስትናገር በሰማኋቸውን ቃላቶች ተውኔቶቼን አስጊጬባቸዋለሁ። እሷ እኔ ላይ ስትጽፍ ነበር። እኔንና ታናናሽ እህቶቼን ፥ የሷንም የአባታችንም ቦታ ሞልታ ፥ ጥርሷን ነክሳ ፥ መንገድ እንዳንስት አድርጋ ፤ ጠብቃ ለዚህ አብቅታናለች። እሷን ለማመስገን ጊዜንና አቅምን ስንጠብቅ ፥ ጊዜ እየቀደመን ተቸገርን። እናም ቆረጥንና ባያችሁን መንገድ እናታችንን አመሰገናት።

https://youtu.be/ie-yY2XnIwk?si=8m0vHas9GcDP_xtJ

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

13 Nov, 21:47


የአንጋፋው የክራር ሙዚቃ መሳሪያ ተጨዋች መሰለ አስማማው የቀብር ሥነሥርዓት ዛሬ ተፈፀመ!

(ይትባረክ ዋለልኝ)

#Ethiopia | የአንጋፋው የክራር ሙዚቃ መሳሪያ ተጨዋች የነበረው መሰለ አስማማው የቀብር ሥነ ሥርዓቱም ዛሬ ረቡዕ ሕዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም በየካ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቹ ዘመዶቹ ጓደኞቹ የሙዚቃ ባለሙያዎች እና ጥቂት ድምፃዊያን ጋዜጠኞች በተገኙበት ተፈፀሟል ፡፡

የመሰለ አስማማው የቀብር ስነስርዓት በየካ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ቀሳውስትና ዲያቆናት በሙያው ብዙ ለሐገሩ ለሰራና ለደከመ ለአንድ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ሐይማኖት ተከታይ የሚደረገውን ስርዓት በማድረግ ቤተክርስቲያኒቱ በክብር ሽኝት በማድረግ ስርዓተ ቀቡሩም እንዲፈፀም አድርጋለች::

በቀብር ስነስርዓቱ ላይ በነበረው ፕሮግራም የመሰለ አስማማው የህይወት ታሪክ ከመቅረቡ ውጪ አንድ ሙዚቃ ባለሙያ ሲያርፍ ሁልጊዜ በየቀብሩ እንደምናየው አይነት የሐዘን መግለጫ የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማህበርም ሆነ መሰል ተቋሞችና ታዋቂ ግለሰቦችም በሽኝቱ ፕሮግራም ላይ ምንም አላሉም::

ሌላው የሙዚቀኛ መሰለ አስማማውን በሙዚቃ መሳሪያዎችና በክራር የተቀነባበሩ የሙዚቃ ስራዎቹን በፈለጉት ሰዓት ላሻቸው ጉዳይ የሚጠቀሙበት የሐገራችን ሚዲያዎች ዛሬ የዚህን ሰው የቀብር ፕሮግራም ለመዘገብ ቸግሯቸዋል::

በመሰለ የቀብር ፕሮግራም ላይ ከአንድ የቴሌቪዥን ጣቢያ እና ከእኔ /ትርታ ኤፍ ኤም/ ውጪ የተገኝ ሚዲያ አልነበረም ::

ይህ ጉዳይ እጅግ ያሳዝናልም እንደሐገርም የሚያሳፍር ተግባርም ነው:: ይህን ያህል ህዝብ እንዲመጣ የሆነውም በማህበራዊ ሚዲያ አማካኝነት የተሰራው ዘገባ እንጂ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ጣቢያዎች አንድም ሥራ የለም::

በነገራችን ላይ ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን መሰለ አስማማው ከታመመበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ሞቱ ድረስ መረጃውን ለህዝብ በማድረስ ስላደረከው ሙያዊ ሐላፊነት በአክብሮት ላመሰግንህ እወዳለሁ::

በመጨረሻም

መሰለ አስማማው በታመመበት ጊዜ ከካናዳ እየተመላለሰች ስታስታምመው ለነበረችው አንድ ልጁ ቃልኪዳን አስማማው እግዚአብሔር መፅናናቱንና ብርታቱን ይስጥሽ::

እንዲሁም ከባህር ማዶ እና እዚሁ ሐገር ሁናችሁ ገንዘባችሁንና ጊዜአችሁን ሰጥታችሁ ሆስፒታል ድረስ ተመላልሳችሁ ላስታመማችሁ ቤተሰቦችና ጓደኞች እግዚአብሔር ብድራችሁን ይክፈላችሁ:: መጽናናቱን ይስጣችሁ !!

እግዚአብሔር የመሰለን ነፍስ በገነት ያሳርፍ፡፡

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

10 Nov, 20:43


"ሿሿ" - ከሰረቋቸው 9 ሞባይል ስልኮች ጋር እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል

#Ethiopia | ሿሿ ተብሎ የሚጠራውን ወንጀል በተለያዩ ቦታዎች ሲፈፅሙ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ

ግለሰቦቹ ወንጀሉን ሲፈፅሙ በቁጥጥር ስር የዋሉት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አየር ጤና አካባቢ እና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ጥሩነሽ ቤጂንግ አካባቢ ነው።

በከተማችን አዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች በተለምዶ አጠራሩ ሿሿ ተብሎ የሚጠራውን የወንጀል አይነት አስቀድሞ ለመከላከል እያከናወነ ያለውን ስራ አጠናክሮ መቀጠሉን የገለፀው የአዲስ አበባ ፖሊስ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 አየር ጤና አካባቢ በኮድ 3 20947 ኦሮ በሆነ ተሽከርካሪ ሁለት ተጠርጣሪዎች ካልተያዙ ግብረ አበሮቻቸው ጋር ወንጀሉን ሲፈፅሙ በፖሊስና በአካባቢው ህብረተሰብ ተባባሪነት ከሰረቋቸው 9 ሞባይል ስልኮች ጋር እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል ብሏል።

በተመሳሳይ ዜና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማም ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 9:00 ሠዓት ገደማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ጥሩነሽ ቤጂንግ አካባቢ የታክሲ ሾፌር፣ ረዳትና ተጓዥ በመምሰል በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 በሆነ 26019ደሕ ሚኒ ባስ ተሽከርካሪ አንድ መንገደኛ ሴት ካሳፈሩ በኋላ የያዘችውን ሳምሰንግ የእጅ ስልክና 20 ሺ ብር በመቀማት በኃይል ገፍትረው በመጣል ለማምለጥ ሲሞክሩ በስራ ላይ በነበሩ የታክሲ ተራ አስከባሪዎችና የፖሊሰ አባላት ከነ ኤግዚቢቱ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውንም የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

በተለምዶ ሿሿ እየተባለ የሚጠራው የማታለል ወንጀል የሚፈፀመው በትራንስፖርት ተሽከርካሪ መሆኑን ያሳሰበው ፖሊስ ህብረተሰቡ ትራንስፖርት ሲጠቀም ተገቢውን ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚጠበቅበት ገልፆል።

በእነዚን ግለሰቦች ወንጀል ተፈፅመብኝ የሚል ለክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያዎቹ ጥቆማ በመስጠት ወይም ተጨማሪ መረጃ በመሆን ተባባሪ እንዲሆን ፖሊስ አስታውቋል፤ አያይዞም የሞባይል ስልክ የተሰረቀበት ግለሰብ ወደ ፖሊስ መምሪያዎቹ በአካል በመምጣት መምረጥ ይችላልም ብሏል።

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

02 Nov, 21:15


🇺🇸 ኒውዮርክ_ማራቶን በነገው ዕለት ለ53ኛ ጊዜ ይካሄዳል

* ኢትዮጵያውያን የረጅም ርቀት አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ለአሸናፊነት ይጠበቃሉ።

#Ethiopia | አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የመጀመሪያ የማራቶን ውድድሯን ከአስር ዓመት በፊት ለንደን ላይ ነበር ያደረገችው። የኦሊምፒክና የዓለም ሻምፒዮና ባለድሏ አትሌት በነገው የኒውዮርክ ማራቶን ትፎካከራለች።

ከጥሩነሽ በተጨማሪ በዚህ ውድድር ኬንያዊቷ የፓሪስ ኦሊምፒክ የማራቶን የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊ አትሌት ሔለን ኦቢሪ፣ ኢትዮጵያውያኑ አትሌቶች ሰንበሬ ተፈሪና ዴራ ዲዳ ለአሸናፊነት የሚያደርጉት ፉክክር በጉጉት ይጠበቃል።

በወንዶች የኦሊምፒክ ሻምፒዮኑ አትሌት ታምራት ቶላ ያለፈው ዓመት የኒውዮርክ ማራቶን አሸናፊ ሲሆን የቦታውን ክብረወሰን በ2:04:58 ሰዓት ከአስራ ሁለት ዓመት በኋላ ማሻሻሉ አይዘነጋም።

ኢትዮጵያዊው አትሌት አዲሱ ጎበና፤ ባለፉት ሁለት ኦሊምፒኮች በርቀቱ ሜዳሊያ ውስጥ በመግባት ጠንካራ ተፎካካሪ መሆኑን ያስመሰከረው ቤልጂየማዊው አትሌት አብዲ በሽር የታምራት ብርቱ ተፎካካሪዎች ይሆናሉ ተብሏል።

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

31 Oct, 21:29


257 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲወጡ የውሳኔ ሐሳብ ተሰጠ

#Ethiopia | በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የይቅርታና ምኅረት ቦርድ 257 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲወጡ የውሳኔ ሐሳብ መስጠቱን አስታወቀ፡፡

በፍትሕ ሚኒስቴር የይቅርታና ምኅረት ቦርድ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተወካይ ዐቃቤ ሕግ ወይኒ ገብረሚካኤል በሰጡት ማብራሪያ÷ ከይቅርታና አመክሮ አፈፃፀም ጋር በተያያዘና የይቅርታ ቦርዱ የውሳኔ ሐሳብ የመስጠትና የማፀደቅ ሥራን አስመልክተው በሩብ ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራትን አብራርተዋል፡፡

በሰጡት ማብራሪያም ቦርዱ ከፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን እና ከክልል ፍትሕ ቢሮዎች ወይም ጠቅላይ ዐቃቤ ሕጎች የቀረቡ የይቅርታ ጥያቄ የውሳኔ ሐሳብ የተሰጠባቸውን 402 የፌዴራል ታራሚዎች የይቅርታ ጥያቄ መመርመሩን ገልጸዋል፡፡

ከምርመራው በኋላም 257 ታራሚዎች በይቅርታ እንዲወጡ የውሳኔ ሐሳብ በማሳለፍ በኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ፀድቆ ተፈፃሚ ሆኗል ማለታቸውን የፍትሕ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡

እንዲሁም ቦርዱ የ89 ታራሚዎች የይቅርታ ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን እና 51 ታራሚዎች ደግሞ በቦርዱ ትዕዛዝ የተሰጠባቸው መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

23 Oct, 04:07


አልሀምዱሊላህ!
በውሳኔህ ተሳስተህ አታውቅም !

#Ethiopia | ብዙ ሰተኸኝ ነበር ጥቂት ወስደህብኛል ክብርና ልቅና ላንተ የተገባ ይሁን!

አሁንም ቢሆን የጉዳት መጠናችን በውል አልታወቀም ቢሆንም የብዙዎች ወንድሞቼ ንብረት በአጠቃላይ በሚባል መልኩ ወድሟል አላህ ለሁላችንም መፅናናትን ይስጠን የተሻለውን አላህ ይተካልን!!

ሲቀጥል ብዙዎቻችሁ CBE account እየተቀባበላችሁ ልታግዙኝ እየሞከራችሁ ነው!!! በጣም አመሰግናለው!! ግን እኔ ከብዙ አላህ ከሰጠኝ ፀጋ በጥቂቱ ስለሆነ የነካኝ ለኔ የምታረጉትን ገቢ ለወንድሞቼ እንድታረጉ በትህትና እጠይቃለው!!!

እንዲሁም የኔን የለጠፋችሁትን እንድትሰርዙት በአክብሮት እጠይቃለው!!!!

ሐሩን ሰዒድ

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

21 Oct, 14:21


"የአልኮል ሱስ ህይወቴን አመሰቃቅሎብኛል ፤ ካሁን በኋላ አልኮል ስጠጣ ካገኛችሁኝ ግደ*ኝ "

#Ethiopia | ተወዳጁ ድምጻዊ  ያሬድ ነጉ ሰይፉ ሾዉ ላይ ቀርቦ ሕይወቱን እስከማመሰቃቀል የደረሰ የአልኮል እና ተጓዳኝ ሱሶች ተገዝዥ እንደሆነ ተናዟል ።

ፈፅሞ ድምፃዊ የያሬድ ነጉ ከምናየው መልክ ተቀይሮ የመጣበት እጅጉኑ አንጀት የሚበላ ሰው ሆኖ መቷል ፡፡ ታላላቅ በተለያየ ዘርፍ ያሉ አርቲስቶች ሰዎች በቴሌቪዥን መስኮት ብቻ ስንመለከታቸው ፍፁም ደስተኛ ስኬት አልጋ በ አልጋ የመጣ እና ምንም ነገር የማያስጨንቃቸው ይመስለናል ፍፅሞ ግን ስህተት ነው ፡፡

በፊት የነበረው የያሬድ ነጉ ባሕሪ ያሳለፈው የሕይወት መልክ በአንድ አጋጣሚ ቆም ብሎ ሲያየው ከንቱ አልባ መሆኑን ሲያውቅ ፀፀቱ በውስጥ አንገብግቦታል ፡፡ አርቲስት ሕይወቱን እስከማመሰቃቀል የደረሰ የአልኮል እና ተጓዳኝ ሱሶች ተገዝዥ እንደሆነ ተናዟል ። ድምጻዊው የቅርብ ወዳጆቹን ፣ አብሮ አደጎቹን ፣ የልጅነት ፍቅረኛውን ጭምር በዚህ ምክንያት እና ዝናውን መሸከም ክብረት ማጣቱን በእንባ ጭምር ተናግሯል ።

ተወዳጁ ድምጻዊ ከባድ የሚባል የአልኮል ሱስ ውስጥ እንደቆየ  አስታውሶ  ፣ አሁን ግን በፈጣሪ እርዳታ ከዚህ ሕይወት ነጻ መውጣቱን ተናግሯል ። ሁለተኛ መጠጥ አልጠጣም ሲጠጣ ካገኘኸኝ ግደለኝ ብሏል ።

ትከሻው ዝና እና ገንዘብን መሸከም አቅቶት ብዙዎችን አስቀይሜያለሁ ። ለዚህም ይቅርታ ጠይቋል  ። ዝነኞች ዝናን መሸከም የሚችል ትከሻ ሊኖራቸው ይገባል ሲልም መክሯል ።
በቅርቡ አዲስ የበኩር አልበሙን  በራሱ ዩቱብ ቻናል ጭኖ ያደርሰናል በርካታ ሰዎች ተሳትፈዋል ፋኑ ጊዳቦ ፣ስማገኘሁ ሳሙኤል እና ሌሎች አዳዲስ መጣቶች ያሉበት "ላሎዬ" የተሰኘ አልበሙን ያደርሰናል፡፡ አይዞን ወዳጄ ብዙ ነገር ይታለፋል አርቲስት ቀን ከፍ ያደርገዋል፡፡

ይቅናህ ወዳጄ ያሬድ ነጉ ፡፡

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

19 Oct, 21:18


ምንም ጉዳት ሳያደርስ እሳቱ ጠፍቷል!

#Ethiopia | ምንም ጉዳት ሳያደርስ እሳቱ በአጭር ጊዜ ሊጠፋ ችሏል፤ ሁሌም ከጎናችን ስላላችሁ ከልብ እናመሰግናለን፡፡

ወንድማችሁ ቢንያም በለጠ

#Ethiopia | ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 09 ቀን 2017 ዓ/ም ፤ አያት ጸበል አርባ ዘጠኝ ቁጥር አውቶብስ ማዞሪያ በሚገኘው በሜቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማዕከል ውስጥ ፤ በወገኖቻችን ትብብር በመሰራት ላይ ባለው አዲሱ ህንጻ ውስጥ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት አካባቢ መጠነኛ የእሳት ቃጠሎ ተከስቶ የነበረ ቢሆንም በፈጣሪ ታምር፣ በማዕከላችንና አካባቢው ኗሪዎች እንዲሁም በእሳት አደጋ ባለሙያዎች ርብርብ እሳቱ ምንም ጉዳት ሳያደርስ በአጭር ጊዜ ሊጠፋ ችሏል፡፡

እሳቱ የከፋ ጉዳት ሳያደርስ በአጭር ጊዜ እንዲጠፋ ላስቻላችሁና ለተጨነቃችሁ ሁሉም ወገኖቻችን ከልብ እናመሰግናለን፡፡
ወንድማችሁ ቢንያም በለጠ

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

16 Oct, 21:05


ጅግጅጋ : በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የሆነውን ነጻ የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት ሊሰጥ ነዉ

#Ethiopia | ታዝማ የውስጥ ደዌና የቀዶ ህክምና ልዩ ማዕከል ከጥቅምት 08 – 10 2017 ዓ.ም በጅግጅጋ ከተማ ‘ሸኽ ሀሰን ያባሬ ኮንፕሬሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል” ነጻ የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለማድረግ የታዝማ የህክምና ቡድን ዛሬ ወደ ስፍራዉ አቅንተዋል፡፡

ይህ ሚሽን ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጲያዊያን የህክምና ባለሙያዎች ታቅዶ በአገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚከናወን ሲሆን 10 ለሚሆኑ ህፃናት እና አዋቂ የልብ ህሙማንን ህይወት ለምታገድ ያለመ የበጎ አድራጎት ተግባር ነዉ፡፡

ይህ የበጎ አድራጎት ተግባርም ለወደፊት ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ሲል ታዝማ የውስጥ ደዌና የቀዶ ህክምና ልዩ ማዕከል ገልፆል::

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

10 Oct, 21:40


የፍቅር ስጦታ ❣️

ቁጥር ~ 39 ~

#Ethiopia | “ የልጆቼን ትምህርት ቤት መክፈል አቅቶኛል” የሙዚቃ ቪዲዮ ዳይሬክተር ስንታየሁ ሲሳይ

የሙዚቃ ዳይሬክተር ስንታየሁ ቁጥራቸው የበዙ ዘመን ተሻጋሪ የሙዚቃ ክሊፖችን ሰርቷል።
📌 የሄለን በርሄ - ልቤ እና እስኪ ልየው፣
📌 የዳን አድማሱ - ከፍቶሽ እንዳላይ ፣
📌 ደሜ ሉላ ሉላ እና ዱምባ ዱምባ
📌 ሙዳ ሼዳ እና ሳሮን ተፈሪ - ሚሶ ነጋያ ፣
📌 የጥበቡ ወርቅዬ - ሊጋባ ፣
📌 የመስፍን በቀል - ደመላሽ ፣
📌 ፍቅርአዲስ ነቃጥበብ ፣
📌 ኃይልዬ ታደሰ - ድሬ ድሬ፣
📌 የላፎንቴኖችን ባቡሬ ፣
📌 ነፃነት መለሰ - ደጉ ባላገሩ እና የታለ ልጁ የታለ፣
📌 ንጉሡ ታምራት - Ijaan Nalaaltee ,
📌 ሸዊት መዝገቦ - ፀማዕኻኒ
📌 ኤዴን ገብረ ሥላሴ - ሰው ዋኖ
📌 ገረመው አሰፋ - አለ ወይ
📌 ትንሳኤ ጎበና - ሰማይ
📌 ወንድሙ ጅራ - ከራስ ጋር
📌 ዘለቀ ገሠሠ - ሀገሬ እና ሌሎች በርካታ ክሊፖችን ወዘተ🙏 ሰርቷል

“..ለገንዘብ ሰርቼ አላውቅም ፤ ዘመን የሚሻገር ስራ ነው መስራት የምወደው ፣ ያላመንኩበትን ሥራ መስራት አልወድም” የሚለው ስንታየሁ ዛሬ ላይ ዋጋ እንዲከፍል እንዳደረገው ገልጿል ። ልጆቹን ለማሳደግ መኪናውን እስከመሸጥ መድረሱን ተናግሯል ።

ስንታየሁ በአሁን ሰዓት የልጆቹን ትምህርት ቤት መክፈል አቅቶት ልጆቹ ትምህርታቸውን ሊያቆሙ እንደሆነ ጭምር በEBS ቅዳሜ ከሰዓት ፕሮግራም ላይ ቀርቦ የእንባ ሳግ እየተናነቀው ተናግሯል።

አንጋፋውን የጥበብ ባለሞያ፤
ስንታየሁ ሲሳይ ወልደ ፃዲቅን ለማገዝ
1000351511285 - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
5141003450005 - ዳሽን ባንክ
73749093 - አቢሲኒያ ባንክ

https://gofund.me/5cd8a047

***
እጅ ነስተናል!

አርቲስት እመቤት ወ/ ገብርኤል ( ከአሜሪካ 🇺🇸 ) ፥ የፍቅር ስጦታቸውን አበርክተዋል።

እናመሰግናለን 🙏❤️

ሀሙስን- ለፍቅር ስጦታ ያዉሉ።

Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን) - ሚዲያና ኮሙኒኬሽንስ የፍቅር ስጦታ የሚያበረክቱትን ስም ዝርዝር ይዤ እመለሳለሁ።

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

10 Oct, 21:39


6ኛው የኢሬቻ ፎረም በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው

#Ethiopia | ስድስተኛው የኢሬቻ ፎረም አዲስ አበባ በሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው፡፡

በፎረሙ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የፌደራልና የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ አባ ገዳዎች፣ ሃደሲንቄዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው ተገኝተዋል፡፡

ፎረሙ እየተካሄደ የሚገኘው "ኢሬቻ ለባህላችን ህዳሴ" በሚል መሪ ሐሳብ ነው፡፡

Getu Temesgen (ጌጡ ተመስገን)

29 Sep, 09:46


የዘመሙ ጎጆዎችን እያቃናን የሚፈሱ እንባዎች ሲታበሱ ማየት እጅግ ደስ ያሰኛል!

#Ethiopia | ዛሬ በአዲስ ከተማ ክፍለከተማ ዊንጌት እና ገብስ ተራ አካባቢ ደሳሳ የሆኑ የቀበሌ ቤቶችን በማፍረስ ለመኖር ምቹ እና ለሰው ልጅ የሚመጥኑ 75 የመኖሪያ ቤቶች ያላቸው ባለ 5 ወለል(G+5) ሁለት ህንጻዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ገንብተን ለነዋሪዎቻችን አስተላልፈናል::

ዛሬ ያስተላለፍናቸው ምቹና ፅዱ የመኖሪያ ቤቶች በመሃል ከተማ የተገነቡ፣ የመጸዳጃና የማብሰያ ቦታ እንዲሁም ሰፋፊ ክፍሎች ያላቸው ሆነው የተለወጡት ቤቶች ከዚህ ቀደም ለመኖር ቀርቶ በዚያ ለማለፍ እንኳን ይከብዱ የነበሩ ሲሆን የመኖሪያ ቤቶቹ ከቦታው ከተነሱ ነዋሪዎች በተጨማሪ ለልማት ከመኖሪያ አካባቢያቸው ለሚነሱ ዜጎቻችን የሚተርፉ ሆነው በጥሩ ሁኔታ ተገንብተዋል::

ልማቱ ነዋሪዎቻችንን የዘመናዊ መኖሪያ ቤት ባለቤት እና ምቹ በሆኑ የመኖሪያ አካባቢዎች የመኖር እድልን የሚፈጥርላቸው ሲሆን ራዕያችንን በመጋራት ቤቶቹን ለመገንባት የደገፋችሁን እና ያስተባበራችሁ አካላትን በሙሉ በተለይም የብዙአየሁ ታደለ ፋውንዴሽን፣ መተባበር ለኢትዮጵያ አ/ማ፣ ተምሳሌት በሲዳሞ ተራ አ/ማ፣ ምዕራብ ገበያ ልማት አ/ማ፣ ጉሊት አክሲዮን ማህበር፣ ሸራ ተራ ብርሃን አክሲዮን እንዲሁም ጎሽ ንግድና አክሲዮን ግንባታ ማህበርን በተጠቃሚ ነዋሪዎች እና በከተማ አስተዳደራችን ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ::

ስንተባበር የሰው ኑሮ እና አኗኗርን እያሻሻልን ሀገር እንገነባለንና ትብብራችንን አጠናክረን እንቀጥል!

ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ