Ethio 251 Media @ethio251media Channel on Telegram

Ethio 251 Media

@ethio251media


ETHIO 251 is an independent media offering you News, Political Analysis and Information feeds. መረጃ ለማድረስ :- @Ethio251MediaInfo

Ethio 251 Media (English)

Are you looking for a reliable source of news, political analysis, and information feeds? Look no further than Ethio 251 Media! This independent media channel provides a platform for individuals who are eager to stay informed about the latest happenings in Ethiopia and beyond. With a commitment to delivering accurate and timely content, Ethio 251 Media ensures that its followers are always up-to-date with the most important news stories. Whether you are interested in politics, current events, or simply want to enhance your knowledge, this channel has got you covered. By joining Ethio 251 Media, you will have access to insightful commentary, breaking news updates, and a variety of informative content that will keep you engaged and informed. Stay connected with Ethio 251 Media to stay ahead of the curve and join a community of individuals who are passionate about staying informed. Follow @Ethio251MediaInfo for more details and to get started on your journey towards becoming a well-informed individual.

Ethio 251 Media

18 Feb, 16:35


የአደረጃጀት ዜና!

የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አመራሮች እና የ8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አመራሮች በደባይ ጥላትገን ወረዳ የሚገኜው ደባይ ጮቄ ብረጌድ አመራሮችና አባላት ሁለት ቀን የፈጄ ውይይት በደባይ ጥላትገን ወረዳ ደብረ እየሱስ ከተማ አካሂደዋል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ም/ል ሰብሳቢ እና ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው፣ ዘመቻ መምሪያ ሀላፌ መቶ አለቃ አበበ ሰው መሆን፣ የሰው ሀይል አስተዳደር መቶ አለቃ እሱባለው ዋለ እንዲሁም የፖለቲካ መኮነኖች እና የ8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አመራሮች በደባይ ጥላትገን ወረዳ ደብር እየሱስ ከተማ በመገኜት ከደባይ ጮቄ ብርጌዱ አመራሮች፣ የሻለቃ አመራሮች የፋኖ አባላት በወረዳው ውስጥ የግል መሳሪያ ይዘው የነበሩ የሆላ ደጀን የህብርተሰብ ክፍሎች ጋር በመገኜት የደባይ ጮቄ ብርጌድ ወታደራዊ አደረጃጀት ወታደራዊ ዝግጁነት በብረጌዱ በተፈጠረው ወቅታዊ ችግሮች ለመፍታት ሁለት ቀን የፈጄ ውይይት አካሂደዋል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የሚያወጣቸውን መመሪያዎች ያለምንም የመረህ ጥሰት በአግባቡ እንዲተገበሩ የ8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አመራሮችን እና የደባይ ጮቄ ብርጌድ አመራሮችን በተሰጣቸው የሰራ ዘርፍ በመገምገም በድረጅቱ የመጡ መምሪያዎች እና ደንቦችን እንዲተገበሩ ከተቋሙ አሰራር ውጭ መረህ ጥሶ የሚሰራ አመራር በተቋሙ እንደሚጠየቅ በማስረዳት የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን በመስጠት ውይይቱ በሰላም ተጠናቋል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ይበልጣል ጌቴ

አዲስ ትውልድ!አዲስ ተስፋ!አዲስ አስተሳሰብ! ለአማራ ህዝብ!

Ethio 251 Media

18 Feb, 14:50


ሰበር የድል!

በሸዋ ክፍለ ሀገር መርሀቤቴ አውራጃ ከአለም ከተማ ቅርብ ርቀት ላይ የአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር ተወርዋሪ እሳተ ገሞራ ሻለቃ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ባደረገው የደፈጣ ውጊያ ከፍተኛ ጀብዱ ፈፀመ።

ራሱን ጥምር ጦር ብሎ የሚጠራው የአገዛዙ ሰራዊት የተለመደ ተግባሩን ማለትም የአማራን ህዝብ ለማሰቃየት እንቅስቃሴ እያደረገ ባለበት ሁኔታ ከመርሀቤቴ አለም ከተማ ቅርብ ርቀት ጌብ ዘሞይ ቀበሌ ልዩ ስሙ አትለፊኝ በተባለ ቦታ ላይ ከቀኑ 5:20 እስከ 7:30 ድረስ በተደረገ የደፈጣ ውጊያ እና ወደ ኋላ ስቦ በመምታት ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ የአገዛዙ ሰራዊት ተደምስሰዋል።
ናደው ክፍለ ጦር በመከረበት በዋለበት በተንቀሳቀሰበት ሁሉ ጠላት ይሸበራል ይሸማቀቃል ውሎም አያድርም የምንለው በምክንያት ነው።

ናደው ክፍለ ጦር እንደ አለት የጠነከረ ክፍለ ጦር እንዲሆን በወታደራዊና በፖለቲካዊ ብስለት በወኔና በጀግንነት ሰርቶ በርካታ የጠላት ሰራዊትን እስከወዳኛው ሸኝቶ እንደ አፄ ቴወድሮስ ራሱን የሰዋው ቀኝ አዝማች ይታገሱ አዳሙ መስዋዕትነት የከፈለባት ቦታ ላይ ነው በአናብስቶቹ የናደው ክፍለጦር ተወርዋሪ እሳተ ገሞራ ሻለቃ የሰራዊት አባላት የተቀጠቀጠው።

በዚህም የተነሳ አለም ከተማ ላይ የተቀመጡት ከፍተኛ የስርአቱ ወታደራዊ አመራሮች ከፍተኛ ጭንቀትና ብስጭት ውስጥ እንደገቡ ለማረጋገጥ ችለናል።

ኦፕሬሽኑ መታሰቢያነቱ ለአርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገስ አዳሙ ነው።

ይህ ኦፕሬሽን በጦር ጠበብቶቹ በአማራ ፋኖ በሸዋ ዋና ጦር አዛዥ አርበኛ ፊታውራሪ ባዩ አለባቸውና በናደው ክፍለጦር ምክትል አዛዥ ለአስተዳደር አርበኛ ቀኝ አዝማች አቡ አሳመረው እንዲሁም ግዳጁን በፈፀመችው ሻለቃ አዛዥ አርበኛ ፋኖ አብርሀም ተስፋዬ የተመራ ውጤታማ ኦፕሬሽን ነው።

ክብር ለተሰውት ሰማዕታት
ድላችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ
የካቲት11/2017ዓ.ም

ከአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል

Ethio 251 Media

18 Feb, 11:11


ጥር 29/2017 ሰከላ ወረዳ ጓልሳ ቀበሌ ላይ በተደረገው አውደ ውጊያ የ73ኛ ክፍለጦር መሪ የሆነው ኮሎኔል ድባቤ በግዮን ብርጌድ ከፍተኛ ኪሳራ አጋጥሞት ነበር። በዚህ አውደ ውጊያ ሁለት ሻምበል መሪዎች የተማረኩ ሲሆን አንድ ሻምበል መሪ ከብዙ አባሎቹ ጋር በአናብስቶቹ ግዮን ብርጌድ ተደምስሷል። ከጥር 29/2017 ጀምሮ በቀን ከ5-10 የሚሆኑ እግረኛ እስከ ሜካናይዝድ የአገዛዙ አባላትም እየከዱ ይገኛል።

ኮሎኔል ድባቤም በደረሰበት ኪሳራ ከጥር 29/2017 ጀምሮ በከፍተኛ ህመም እና ጭንቀት ውስጥ ይገኛል። ድባቤ ሰከላ ወረዳ ከሚገኙ የግልም ሆነ የመንግስት ጤና ጣቢያ ህክምና ሲከታተል ቢቆይም ሊሻለው ባለመቻሉ በዛሬው ዕለት ወደ ቲሊሊ ተሸኝቷል።

ጠላት ከሰከላ ኮሎኔል ድባቤን ተቀብሎ ወደ ቲሊሊ እየተመለሰ ባለበት ሰአት አይበገሬዎቹ የሰከላው ግዮን ብርጌድ መብረቁ ሻለቃ፣ ናደው ሻለቃ እና የቲሊሊው ዘንገና ብርጌድ በአንድ ላይ ጥምረት በመፍጠር እና ደፈጣ በመያዝ ቲሊሊ መግቢያ በጠላት ላይ መብረቃዊ ጥቃት ሰንዝረዋል። በዚህ ጥቃትም በርካታ የጠላት ሀይል ሙት እና ቁስለኛ ሆኗል። በዚህ አውደ ውጊያ ከ4:00-7:30 የተደረገ ሲሆን በወገን ሀይል ላይ ምንም አይነት ጉዳት አልተመዘገበም።


የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ኛ ክፍለጦር የግዮን ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት ፋኖ የቻለ አድማሱ

ድል ለተገፋው ለአማራ ህዝብ
ድል ፋኖ!

አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋን

Ethio 251 Media

18 Feb, 10:39


የአማ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር ዘንገና ብርጌድ ቲሊሊ︎ የዉጊያ ዉሎ!!

የአሸባሪው መንግስ ወንበር አስጠባቂው ወንበዴዉ በድን ዛሬ በጠዋቱ ከቲሊሊ ተነስቶ ከወደ ሰከላ የመጣውን ኮረኔል ለመቀበል በተንቀሳቀሰበት ጊዜ የቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ደን ስላሴ ተብሎ ከሚጠራው ቦታ እስከ ቲሊሊ ከተማ ድረስ ከበባ በማድረግ ድባቅ መቶታል።

ቡድኑ እንደተለመደዉ አንድ ያለችውን ማስፈራሪያ ዙ23 ከእንጅባራ በማምጣት ድሽቃዎችን ጭምር ቢጠቀምም ከመቀጥቀጥ ከመሮጣ አላዳነውም።

ከጥዋቱ 4:00 ጀምሮ እስከ 7:00 በዘለቀው አውደ ዉጊያ 15 የሚደርሱ እንከፎች እስከወዲያኛው ተሸኝተዋል። ቀሪው ቁስለኛው እየተሸከመ ነፍሱ እስክትወጣ እሩጦ ከሚቀበርበት ጉድጓድ ገብቷል።

ይህ ሀይል ሽንፈቱን ለመበቀል መንገድ ላይ የሚያገኛቸውን ንፁሃን ማህበረተሰብ አፍኖ ወስዷል። በነበረዉ ተጋድሎ ከግዮን ሰከላ ብርጌድ መብረቁ ሻለቃ ተወርውራ በመድረስ የተለመደዉን ቅስም ሰበራ ጀብድ ፈፅማለች።

በዚህ ዉጊያ ምንም የወገን ሃይል ጉዳት ሳያስተናግድ አስደናቂ ጀብድ በመፈፀም ተጠናቋል።

ትግላችን እስከ ቀራኒዮ ድላችን እስከ አራት ኪሎ ይቀጥላል።

ላናሸንፍ አልጀመርነዉም︎!!

የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ ክፍለጦር ቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ፋኖ አለበል አወቀ

Ethio 251 Media

18 Feb, 09:21


የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ ክፍለጦር ቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ቲሊሊ ላይ ከተማ ከጠዋቱ 4:00 የጀመረ ዉጊያ እንደቀጠለ ነዉ።

ዘንገና ብርጌድ ትንቅንቅ እያደረገ ይገኛል። ጠላት ከዙ 23 ድሽቃ አስከ ሞርታር ከባድ መሳሪያ ቢያሰልፍም የፋኖን ጥይት መቋቋም አልቻለም።

Ethio 251 Media

17 Feb, 18:50


የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ሸህ ሁሴን ጅብሪል ክፍለጦር እና ንጉስ ሚካኤል ክፍለጦር ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

የምዕራብ ወሎ ኮር ሁለቱ ክፍለጦር አሃዶች የካቲት ዘጠኝ ለአስር ሌሊቱን ገነቴ ከተማ በመግባት ከባድ ትንቅንቅ በማድረግ ታላቅ ድል አስመዝግበዋል::

ከአማራ ህዝብ አብራክ ወጥተው ህዝባቸው ላይ ዘር ማጥፋት ከሚፈፅመው የብልፅግናው መንግስት ጋር ወግነው ያሉ ሚሊሻና አድማ ብተና ያለምንም መሰላቸትና በፍፁም ትዕግስት በፋኖ እየተደረገላቸው ያለዉን ጥሪ ባለመቀበላቸው ገነቴ ከተማ ላይ በተደረገ በዚህ ዉጊያ በርካቶች ሲደመሰሱ ቁጥሩ ቀላል የማይባል ባንዳ ቁስለኛ ሆኗል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
የካቲት 10/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

17 Feb, 17:33


የዛሬ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-

https://twitter.com/i/broadcasts/1YpKkBXjqQAxj

https://rumble.com/v6lxu01--251-251-zare-february-17-2025-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

17 Feb, 15:44


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ለበርካታ ወራት ያሰለጠናቸውን አባት አርበኛ ጦር አስመረቀ!

አደረጃጀት የማዘመንና ሠራዊት የማብቃት ተልዕኮውን በአግባቡ እየተወጣ የሚገኘው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ከግንባር ተጋድሎ ጎን ለጎን የሠራዊት ግንባታ አፈፃፀሙን አጠናክሮ ቀጥሏል።

በትናትናው ዕለትም በጀግናው አርበኛ ማንበግር ንጉስ የተሰየመው ማንበግር ክፍለጦር በቀወት ወረዳ ራሳ ለወራት ያሰለጠናቸውን እርሳስ ግንባር ላይ የሚጥሉ አባት አርበኞችን የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በተገኙበት በድምቀት አስመርቋል፡፡

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ባሉት 8 ክፍለጦሮች ጠንካራ መሠረት ያለው ፤ ለህዝብ ነፃነት የሚዋደቅ ታማኝ ሠራዊት በመገንባት አደረጃጀት እየገነባ ተቋማዊነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል።

ስር ነቀል ለውጥ የትግላችን መዳረሻ ነው!

አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ሚዲያና ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

Ethio 251 Media

17 Feb, 12:38


የድል ዜና!

መሃል ደብረብርሃን ከተማ የሚገኘው አገዛዙ ወታደራዊ ካምፕ በአማራ ፋኖ በሸዋ ነጎድጓድ ክፍለጦር በከባድ ተመታ።

ትናንት የካቲት 9/2017 ዓ/ም እኩለ ሌሊት 7:00 ሰዓት ላይ የአማራ ፋኖ በሸዋ ነጎድጓድ ክፍለጦር አንበሳው ብርጌድ አስራት ሻለቃ በብርጌዱ ዘመቻ መሪ በፋኖ ደረጀ እና በሻለቃዋ መሪ ፋኖ ዳዊት እየተመራ መሃል ደብረብርሃን አፄ -ዘርዓያዕቆብ ክፍለ ከተማ ምድረ ገነት ቀበሌ ሰርጎ በመግባት በአገዛዙ ሰራዊት ካምፕላይ በከፈተው ድንገተኛ ጥቃት ከ15 በላይ የተደመሰሱ ሲሆን ከ20 በላይ ቁስለኛ መሆናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።

በተወሰደው ድንገተኛ ጥቃት የአራዊት ሰራዊቱን ካምፕ ሙሉ ለሙሉ ለሰዓታት መቆጣጠር የተቻለ ሲሆን ቁጥራቸው በዉል ያልታወቁ የሚሊሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ተበትነው መጥፋታቸውን ማረጋገጥ ሲቻል ቁጥሩ በርከት ያለ ምርኮኛ መኖሩን ለማረገጥ ተችሏል።

ከሰሞኑ ጌትቫ ሆቴል የመንግስት ሰራተኞችን በመሰብሰብ ሙሉ ለሙሉ ፋኖን አጥፍተነዋል በማለት የተናገሩት የደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊው በተሰነዘረው ድንገተኛ ጥቃት ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ መግባታቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።

ክብር ለተሰውት!
"ድላችን በክንዳችን"
የአማራ ፋኖ በሸዋ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

Ethio 251 Media

17 Feb, 12:36


የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ባለሽርጡ ክፍለጦር እና ልጅ እያሱ ክፍለጦር ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ምስራቅ አማራ ኮር 1 በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የሚመራው ባለሽርጡ ክፍለጦር እና የልጂ እያሱ ኮር ራስ አሊ ክፍለ ጦር በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ 012 ቀበሌ ልዩ ስሙ አርጎባ በተባለ ቦታ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ፡፡

በተደረገው የህልውና ተጋድሎ የስርዐቱ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ከለሊቱ 10:25 ገዳማ ወደ ቀበሌው ሲያመራ መረጃ የደረሳቸው አይበገሬዎቹ የባለሽርጡ 4ኛ ሻለቃና የራስ አሊ 1ኛ ሻለቃ በያዙት ደፈጣ የወንበር ጠባቂውን ሰራዊት በደፈጣ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ሰርተዋል::

ይህን ተጋድሎ ልዩ የሚያደርገው ከቡድን መሳሪያና ከነፍስወከፍ መሳሪያ ባሻገር በተጋድሎው ጩቤ አና እጂ ለእጂ በመያያዝ እስከ ቦክስ ድረስ በጨበጣ የተደረገ ፊልሚያ ነው::

በዚህ አወደ ውጊያ ከነፍስ ወከፍ መሳሪያ እና ከ2500 በላይ የክላሽ ተተኳሽ መማረክ ሲቻል 12 የሚሆኑ የዙፋን ጣባቂው ሰራዊት እስከ ወዲያኛው ሲደመሰስ 24 የሚሆነውን ሀይል ማቁሰል ተችሏል፡፡

የጀግኖቹን ምት መቋቋም ያቃተው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛውን ሳያነሳ ከሞት የተረፈው ሀይል ወደ ኀላ ከፈረጠጠ ቡሀላ ከጥዋቱ 2:45 ገዳማ በአካባቢው ከባድ መሳሪያ እያሰወነጨፈ ንፁሀንን የሞት ሰለባ በማድረግ ሙትና ቁስለኛውን በአንቡላንስ እየጫነ ወደ ቢስቲማ ከተማ ተመልሷል ሲል የባለሽርጡ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ፋኖ መምህር መሀመድ ሞገስ ገልጿል::

"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማሓራ)
የካቲት 10/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

16 Feb, 13:56


የአማራ ፋኖ በጎጃም የጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር የቢትወደድ አያሌዉ መኮነንን ብርጌድ ለ6 ተከታታይ ወራት ያሰለጠናቸዉን ልዩ ኮማንዶዎች በዛሬዉ ዕለት በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።

በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ የክ/ጦርና ከፍተኛ የእዝ አመራሮች ተገኝተዋል።

በዚህም መሰረት የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር ክ/ጦር ስልጠና መምሪያ ሃላፊ ኮማንዶ ናቲ፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም የሚዲያ ክፍል ባልደረባ ፋኖ ቃል ኪዳን ግርማዉ፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም የዉጭና ዲያስፓራ ግንኙነት ምክትል ሃላፊ ፋኖ ሃይለ ሚካኤል ባየህ፣ የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ፓለቲካ ዘርፍ ሃላፊ ፋኖ ግሩም ምሳሌ በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ የምረቃ ፕሮግራሙ ተከናዉኗል።

ፋኖነት አሸናፊነት

የብርጌዱ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ይበልጣል የዉነቱ (እሳቱ)

Ethio 251 Media

16 Feb, 13:54


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ምስራቅ አማራ ኮር 1 በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የሚመራው ባለሽርጡ ክፍለጦር እና የልጂ እያሱ ኮር ራስ አሊ ክፍለ ጦር በደቡብ ወሎ ዞን ወረባቦ ወረዳ ከአርሶ አደሮች የመሬት ግብር ለመሰብሰብ ከቢስቲማ ከተማ ወደ አረባቲ የተንቀሳቀሰው ሆድ አደር ካድሪ ከእነ አጃቢዎቹ በተያዘ ልዩ የደፈጣ ኦፕሬሽን በመደምሰስና በመበታተን የፋሽስቱ ስርዐት የያዘውን ግብር የማስከፈል አጀንዳ ሳያሳካ ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል፡፡

በተደረገው የህልውና ተጋድሎ የስርአቱ ካድሬ የወረዳው ስላም ስለተመለስ ና በቀጠናው የሚንቀሳቀሰውን የፅንፈኛ ሀይል ስለተደመሰሰ የገቢ ማሰባሰቡን ስራ አጠናክረን መቀጠል አለብን በሚል ተልካሻ ሀሳብ ከቢስቲማ ከተማ ወደ አራባቲ የተንቀሳቀሰው የፋሽስቱ ከድሪ በአጃቢ መልክ የያዛቸው ሆድ አደር ሚሊሻ ጋር በባለሽርጡ 4ኛ ሻለቃ አንድ ሻምበል እና በራስ አሊ ክፍለ ጦር 1ኛ ሻለቃ አንድ ሻንበል በተያዘ ድንቅ ደፈጣ የስርአቱን የካድሬ ስብስብና ሆድ አደር ሚሊሻ ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ሲቻል የተረፈው የተወሰነ ሀይል ወደ መጣበት መመለስ ሲያቅተው ማለትም መመለሻው መንገድ በጀግኖቹ ስለተዘጋበትና መመከት ሲያቅተው እየተበታተነ ወደ አጎራባች አፋር ወረዳዎች ፈርጥጧል፡፡

በተያያዘም የስርዓቱ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ይህን የካድሬ ስብስብ ለማዳን ከሲልኮ ወደ ወረባቦ ቢንቀሳቀስም የሙታን ስብስብን ከማዳን ይልቅ ሙትና ቁስለኛውን እየለቀመ ይገኛል፡፡

የወደቀውና ጣረረ-ሞት ላይ ያለን ስርዐቱ ዳግም ልደቱ ይመጣል ብለው ህዝባችንን ለዳግም ባርነት ለማድረግ ግብር የሚሰበስቡ ኃይሎችን ወደ ፊትም የማያዳግም እርምጃ መውሰዳችን ይቀጥላል፡፡

"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"

የአማራ ፋኖ በወሎ /ቤተ-አማሓራ/ የምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ መምህር መሀመድ ሞገስ

የአማራ ፋኖ በወሎ/ቤተ-አማሓራ/
የካቲት 09/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

16 Feb, 10:58


🔥የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ዓርማ እና የዓርማ ትርጉም‼️

የአማራ ፋኖ በወሎ የድርጅቱ ዓርማ እና የዓርማው ትርጉም ቀጥሎ ተገልጿል፤ ዓርማው የአማራን ሕዝብ መሰረታዊ መገለጫዎች ማለትም የስነ መንግሥት፣ ታሪክ፣ የኢኮኖሚ ስምሪት፣ ፍልስፍና (እሳቤ)፣ የሰላምና ነፃነት ጥበቃ፣ የመሪነትና ሀገር የማስተባበር ሚና የሚወክሉ ይዘቶች ይኖሩታል፡፡ ይህም ጋሻ፣ ክላሽ፣ ብዕር፣ የስንዴ ዘለላ፣ ዘንባባ፣ ንስር፣ መጽሐ እና ጥቁር አንበሳ ይኖረዋል፡፡ የዓርማው መደብ በጥቁርና አረንጓዴ ቀለም የሚቀመጥ ሆኖ የስያሜ ጽሑፉ በወርቃማ ቀለም ተጽፎ የመደቡ ዙሪያ ወርቃማ ቀለም ሆኖ የውስጠኛው መድብ ዙሪያ ደግሞ አረንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀይ ይሆናል፡፡

1.የአሳምነው ምስል፦ የሚያመለክተው አሳምነውነት የአማራ ሕዝብ ትግል ምልክትነትና ርዕዮታችን መሆኑንና ለአማራ ሕዝብ ሲባል በክብር መሰዋት ክብርና ኩራት መሆኑን ለማሳየት የተቀመጠ ነው።

2.ጋሻ እና ክላሽ፡ እነዚህ ምልክቶች ጀግንነትን እና አርበኝነትን የሚወክሉ ሲሆን ከትናንት እስከ ዛሬ የተከፈለን መስዋዕትነት እና በዘላቂነትም የህዝባችንን የሰላም እና ደህንነት ጥበቃ ባህርይ ይገልጻሉ፡፡

3.የስንዴ ዘለላ፡ ይህ ምልክት የግብርና፣ የኢንዱስትሪ እና ምጣኔ ሀብትን የሚወክል ሲሆን የሕዝባችንን አራሽነት ይገልጻል::

4.ንስር፡- ዓርማው ላይ ያለው ንስር የሚያመለከተው የአማራ ሕዝብ ያለውን አርቆ አሳቢነት፣ አስተውሎትና ጠላትን የማጥቃትና የመከላከልን አቅም ለማሳየት ነው።

5.ብዕርና መጽሐፍ፡ ይህ እውቀትን፣ ምርምርን፣ ሐሳብን እና ፍልስፍናን የሚወክል ሲሆን የአማራን ዓለማዊም ሆነ መንፈሳዊ የዳበሩ ፍልስፍናዎች ይገልጻል፡፡

6.አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ የቀለማት ሕብር፡ የሚያመለክተው የኢትዮጵያዊያንን የጋራ ነባራዊ ትስስርን፣ አሁናዊ ትብብርንና የወደፊት ተያያዥ እጣ ፈንታን ነው።

7.ጥቁር አንበሳ፡ የሥነ መንግሥት ወካይ ምልክት ሲሆን በሕዝብ አስተዳደር ውስጥ የመሪነትን እና ተጽዕኖ ፈጣሪነትን ሚና ይገልጻል፡፡ ከኢትዮጵያዊው ጥቁር አንበሳ ጋር ሲጣመር ደግሞ ከሀገረ መንግሥት ግንባታ ጀምሮ ያለንን የመሪነት ሚና ያመለክታል፡፡

8.ወርቃማ ጽሑፍና ክብ፡ የሚያመለክተው በብሩህ ተስፋ የታጀበ እምቅ ሀብትን፣ ረቂቅ ስልጣኔን፣ ጥበብን፣ ኃይልን፣ ግብረ ገባዊነትን፣ ክብርንና እርግጠኝነትን ነው።

9.ጥቁርና አረንጓዴ መደብ፡ አረንጓዴው መደብ የሚያመለክተው የሕዝባችንን የገጸ-ምድርና የከርሰ-ምድር ሐብትና የምድሩንም አረንጓዴነት ሲሆን ጥቁሩ መደብ ደግሞ ባለፉት አምሳ ዓመታትና እስካሁን በሕዝባችን ላይ በኢትዮጵያውያንና በዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ፊት የደረሰበትን የዘር ማሳሳት፣ የዘር ማጽዳትና የዘር ፍጅትን ለማመልከት የተቀመጠ ነው፡፡

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ)
ወሎ፣ አማራ፣ ኢትዮጵያ፤

Ethio 251 Media

15 Feb, 18:51


የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ጎንደሬ በጋሻው ከፍለ ጦር ቴዎዴሮሰ ብርጌድ አሳምነው ሻለቃ በሻለቃ ይርጋ ደሴ እየተመራ በገደብጊያ ዙሪያ መሸጉ በነበረው የጠላት ጥምር ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ በርካታው ሞት እና ቁሰለኛ አድርጎታል።

በተመሣሣይ ሰዓት የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ናሁሰናይ አዳርጌ ብርጌድ በሸለቃ ዋናው እሙሀይ እየተመራ በዳባት በመሸገው የጠላት ሀይል ላይ መብረቃዊ ጥቃት በመክፈት ቁጥሩ ለግዜው የልታወቀ ጠላትን ሙት እና ቁሰለኛ በማድርግ አንድ የዳባት ከተማ ክፍተኛ የብልፅግና በልሰጣንን አንቀው የዘውት ሄደዋል::

በሌላ መረጃ የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር አደዋ ክፍለ ጦር እና ቋራ ኦሜደላ ክፋለ ጦር በጋር በቋራ ግንባር ከጠላት ጋር ሲፋለሙ ውለዋል ::

Ethio 251 Media

15 Feb, 16:59


የዛሬ የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-

https://twitter.com/i/broadcasts/1kvJpyPyVpQxE

https://rumble.com/v6l63aa--251-zare-february-15-2025-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

15 Feb, 14:35


አማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አምሓራ ) ምዕራብ ወሎ ኮር መብረቅ ክፍለ ጦር የደቡብ ወሎ ብልፅግና ዶሮ ጭራ የምታወጣው መላ እና ሴራ ቢያሴርም፣ ሲያሴርበት የነበረው እና ሙሉ የኦፕሬሽን ዕቅዱ በፋኖ እጅ ገብቷል::

በዚህም ዕቅዳቸው ለማስመሰል እና ዋሽተው ለማውራት እና ለማቀድ ቢሞክሩም ከራሳቸው እንኳን እንደሆነው የሥርዓቱ ግባ ተመሬት መድረሱን የሚያሳይ መሆኑን ማየት ችለናል፣ በየዘርፉ ሲገማገሙ እንደነበረው በራሳቸው የውሸት ሥሌት እንኳ በዞኑ ካሉ ወረዳዎች ከ217 በላይ ቀበሌዎችን ፋኖ እንደተቆጣጠረ አጉልተው አሳይተዋል።

ከተወያዩበትም ሥጋት ቆፈን አስገባቸው የፋኖ ዉጤቶች
1. በፋኖ ትግል ሙሉ በሙሉ በሚባል ሁኔታ እንደተሸነፈ አሳይተዋል ::

2. በስሩት የውሸት ዶክመተሪ ቪዲዮ ህዝብ እንደታዘባቸው ታማኝነት እንደጡ አሳይተዋል።

3. የህዝብ ንብረት መዝረፋቸው ከመንግስትነት ይልቅ ዘለፊና ሽፍታ እንደሆኑ አመላክተዋል::

4. በትጥቅና ሬሽን ከፋኖ እንደሚያንሱ አምነዋል::
5. ዞኑን በራሳቸው ፀጥታ ለማስከበር ከአቅማቸው በላይ መሆኑን አምነዋል::

ሆኖም የብልፅግና ወንበር አስጠባቂ ሸምድምድ ቡድን 45 ቀን የሚቆይ የኦፖሬሽን ዕቅዱ ከየካቲት 03 - መጋቢ 30 ዕቅዱን ከመጀመር ይልቅ በጭንቀት ቆፈን ውስጥ ገብቶ እየተርበተበተ ይገኛል::

ባወጣው ዕቅድም ውስጥ አሁንም በዋናነት ንፁህንን የማስቃየት እና የማንገላታት ዋነኛ ዕቃዱ ነው።
ከዚህም መካከል

1. የግለሰብ ትጥቅ መውረስ
2. የፋኖ ዘመድ ቤተሰብ ማሰር ፣ ማስቃየት እና ሀብት ንብረት መዝረፍ፣ ማቃጠል የሚል
3. በፋኖ ስም ማህበረሰቡ ላይ ፀያፍ ስራ በመስራት ፋኖን ከህዝብ መነጠል የሚሉት እና ሌሎች ፀያፍ ድርጊቶች ታቅደዋል።

አሸባሪ ቡድኑ በአጠቃላይ 113 ገፅ ያለው Power Point በሽብር ሥራው አዘጋጅቶ እንደጨረሰ እጃችን ገብቷል።

ከዚህም ተያይዞ የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አምሓራ ) አንድነት ጉባኤ የምዕራብ ወሎ ኮር ባደረገው መብረቃዊ እና አስደንጋጭ የሆነ የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ ወታደር መማረክ እና መደምስስ ተስፋ እንዳስቆረጣቸው ብሎም ከወረዳወች አልፈው ዞኑ ድረስ ማርበትበታቸው ይባስ ምን ማድረግ እንዳለባቸው እንኳን ለማሰብ ተስፋ እንዳስቆረጣቸው ከውስጥ ካሉ ታማኝ የማረጃ ምንጮች ማረጋገጥ ችለናል።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አማራ)
የካቲት 8 ቀን 2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

15 Feb, 11:49


የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ (ቤተ-አማራ) ላስታ አሳምነው ኮር ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር በላስታ ቅዱስ ላልይበላ ከተማ ላይ አስደማሚ ኦኘሬሽን ሰራች።

የካቲት08/2017 ዓ.ም

የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ (ቤተ-አማራ) ላስታ አሳምነው ኮር ካሉት ሰባት(7) ክፍለ ጦሮች ውስጥ አንዷ የሆነችው ነበልባሏ ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር ሻለቃ በረከት ፈንታ ሻለቃ የተመለመሉ ጥቂት ሸማቂ ፋኖዎች የካቲት 07/2017ዓ.ም ከሌሊቱ 6:00 እስከ 7:00ሰዓት ለ1:00 ሰዓት በወሰደ ኦኘሬሽን በላስታ ቅዱስ ላልይበላ ከተማ ላይ ልዩ ቦታው ከተማ አስተዳደር ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ላይ የአገዛዙን ሰራዊት ከፊል ደመናማ አድርጋው ተመልሳለች።

ማንነታችን አሳዳጆቻችን የሚያውቁት እኛም የምናውቀው በኢትዮጽያዊነታችን ተሸፍኖ የኖረው አማራነታችን ነው። አማራ አማራነት...ይህንን ስም ጠላት ይፈራዋል። ጣሊያን እንግሊዝ ግብፆችና ሱዳኖች ስለ አማራ ማንነትና ህዝብ በጀብዱ የተሞላ ታሪክ ፅፈዋል። እናም አሁን ያለው የአማራ ችግርና የሰቆቃ ዘመን የሚያበቃው አንዱ ጥቁር አማራዎችን እንደ አራሙቻ ነቅሎ በመጣል ነውና በላስታ ሰማይ ስር የሚገኙት የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳምነው ኮር ማረጉ ተማረ ክፍለ ጦር ሻለቃ በረከት ፈንታ ሻለቃ የተመረጡ ሸማቂ ተርቦች የአያትና ቅድመ አያቶቻቸውን ታሪክ ለማስቀጠል ቆርጠው የተነሱ ነበልባሎች እሳት ለብሰው እሳት ጎርሰው የአፓርታይዱ ብርሃኑ ጁላን ግብስብስ ሰራዊት ከበባ በጣጥሰው ለጠላት መርዶ ለወገን የኦፕሬሽን አብዶ ሰርተው አንድ ሚሊሻ ለብለብ አንድ ሚሊሻ ተከሽኖ በድምሩ ሁለት የአገዛዙ ሚሊሻዎችን ማርከው ወደ ካዝናቸው ገቢ አድርገው ተመልሰዋል።

የኢትዮጽያውን ኢንተርሃሞይ(Interahamwe) የብልፅግና አምባገነን ስብስብ ድህነትን ጥጋብ ማፍረስን ግንባታ የሚል ከተማን በማብለጭለጭ ድሃን የሚያሰቃይ በህልም አለም ኑሮ እየኖረ በድሃ ስቃይ የሚደሰትን መንግስት ተብየ ወንበር አስጠባቂዎችን የብልፅግና መከላከያ ሃፍረት አከናንበው መረቅ የሆነች ኦኘሬሽን መሃል ከተማ ላይ በብርሃን ፍጥነት ከበባውን በጣጥሰው በፉከራና ሽለላ ታጅበው ተመልሰዋል።

ድል ለመላው ዐማራ ፋኖ
መምህር ቢሆነኝ ቢያበይን
የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ (ቤተ-አማራ) ላስታ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት

Ethio 251 Media

15 Feb, 11:09


ጨፍጫፊው የብልጽግና ሰራዊት በህዝብ መገልገያ ተቋማት ላይ ዘረፋ ፈፀመ።

በየደረሰት ንፁሀንን በመረሸን እና ንብረቶችን በማውደም የሚታወቀው የአብይ አህመድ ስልጣን አስጠባቂ የብርሀኑ ጁላ ጦር በዳንግላ ወረዳ አቫድራ ቀበሌ በህብረተሰቡ መገልገያ ተቋማት እና በግለሰብ መኖሪያ ቤቶች ላይ ዝርፊያ ፈፅሟል።

በተለይ የጨፍጫፊው ጦር ወደ አቫድራ ሲገባ በተደጋጋሚ ንፁሀንን ስለሚገድል የአካባቢው ማህበረብ ከቀበሌው በመውጣት ወደተለያዩ አካባቢዎች ይሰደዳል ለአብነትም ከሳምንት በፊት ወጣት አይተነው ደሴ የተባለ የወንደፋይ ተከስተ ቀበሌ ኑዋሪ እና የ18አመት ታዳጊ በበርሀ እርሻ ቆይቶ ወደ ቤተሰቦቹ ሲመለስ በአገዛዙ ተይዞ በበረሀ ሰርቶ ያጠራቀመውን ብር ከዘረፉ በውሀላ ወጣቱን ገድለው መንገድ ላይ ጥለውታል።

በዚህ የፍርሀት ቆፈን ውስጥ የገባው ህዝብ ቤቱን ጥሎ ሲሰደድ የአገዛዙ ሰራዊት የተዘጉ የግለሰብ ቤቶችን ሰብሮ በመግባት ከፍተኛ ዝርፊ ፈፅሟል ።

በዚህ ዝርፊያ ላይ ከግለሰብ ቤቶች በተጨማሪ የህዝብ መገልገያ ተቋማትም የድርጊቱ ኢላማዎች ነበሩ በዚህም የቀበሌው አገልግሎት ለማህበረብ ለማሰራጨት በማህበር የመጣ ስኳር የአቫድራ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ኮምፒውተሮች የላብላቶሪ እቃዎች እና የአቫድራ ጤና ጣቢያ ሙሉ በሙሉ እና በከፊል ተዘርፈዋል ።

Ethio 251 Media

15 Feb, 09:57


ከአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ) የተሰጠ መግለጫ

ኢትዮጵያዊው ኤዲ አሚን ዳዳ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈፅመው ጭፍጨፋ የሕዝባችንን ትግል አይቀለብሰውም!!!
መንግሥት መር ጭፍጨፋው በሕዝባዊ የፋኖ ትግል ይቀለበሳል!!!

ፋሽስቱና ደም የጠማው የጠራራ ጋኒን አብይ አህመድ በሕዝባችን ላይ የከፈተውን መንግሥታዊ ጦርነትና እየፈፀመ ያለውን የዘር ማሳሳት፣ የዘር ማፅዳትና የዘር ፍጅት የሰማይ አምላክ ካልሆነ በስተቀር የሰው ልጅ በተለይ ኢትዮጵያዊያን የተረዱት ጉዳይ ነው ብሎ ማሰብ ያስቸግራል። አምባገነኑ የብልፅግና ቁንጮ፣ የኢትዮጵያዊያን የዘመናችን ታላቁ መርገም አብይ አህመድ ሲፈልግ በምድር ጦር፣ ሲፈልግ በሰማይ ጀትና በሰው አልባ ድሮን ጥምረት በአማራ ሕዝብ ላይ እየፈፀመ ያለውን ሁለንተናዊ ፍጅት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዐይንና ጀሮ ሳይሰጠው እንደቀልድ ሁለት ዓመት እያለፈው ነው።

የአማራ ሕዝብ በታንክና በመድፍ እንዲሁም በጀትና በሰው አልባ ድሮን ጥምረት የሚጨፈጨፍበት መሠረታዊ ምክንያት የሰው ልጅ በዴሞክራሲያዊው ዓለም ሊከበሩለት የሚፈልጋቸውን ልዩና የዴሞክራሲያዊ መብቶች ስለጠየቀ አይደለም! ወይም የመንገድና መብራት፣ ፋብሪካና ዘመናዊ ከተሞች ስለጠየቀ አይደለም! ወይም በምከፍለው ግብር ልክ ልዩ ልዩ የጤናና የትምህርት ተቋማት ይከፈቱልኝ ስላለም አይደለም! የአማራ ሕዝብ የመብትና የኑሮ ማሻሻያ ጥያቄዎችን ይዞ ሳይሆን የወጣው ሰው ተብሎና ሰው ሆኖ መኖር በመከልከሉ የሕጋዊ ሰውነት እውቅናን፣ የሕግዊ ሰውነት ውክልናን እንዲሁም ተፈጥሮ በሰጠው ዘመን ውስጥ በኢትዮጵያ ምድር ላይ በሕይወት መኖር መቻልን ለመጠየቅ የወጣ ህዝብ ነው፤ መንግሥታዊ ጦርነት የተከፈተበትም ተፈጥሮ በሰጠው ዘመን ውስጥ በሕይወት መኖርን ስለጠየቀ ብቻና ብቻ ነው። የአማራ ህዝብ ጥያቄ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ውሎች ሁሉንም ሕዝብ በኢትዮጵያዊነቱና በሰውነቱ ልክ ይወቁት፣ ይዳኙት፤ እኔንም ሕጋዊ የዜግነት እውቅናና ሕጋዊ የሕዝብ ውክልና ይስጡኝ፣ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋርም እኩል ይዳኙኝ የሚል የመኖር ያለመኖር ጥያቄ ነው። በሕዝባችን ጥያቄ ውስጥ በሀገራችን መንግስት በዘራችን ምክንያት ማንነታችን ሳይከዳ፣ ማንነታችን ሳይሳሳና ሳይጠፋ በሕግ ታውቆ መኖርን፣ እኩልነትን፣ ዲሞክራሲንና ፍትሕን የምናገኝ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት መሠረት ነው። ኢትዮጵያዊያን ግን ልብ ያሉት አይመስልም።

የሰላም ኖቤል ተሸላሚው ሕዝብ ጨፍጫፊውና ጦረኛው አብይ አህመድ ግን እነዚህን የከበሩ የሕዝብ ጥያቄዎች የአማራን ሕዝብ በማንበርከክ ጥያቄዎቹን ድጋሜ እንዳይነሱ ማድረግ ካልሆነም የአማራን ሕዝብ ማጥፋትን ዓላማዬ ብሎ መያዙ ገሃድ የወጣ ሐቅ ነው። በአንዳንድ ፀሐፍት አምባገነኑ ሦስተኛው የዩጋንዳ ፕሬዝደንት ኤዲ አሚን ዳዳ ዘር መርጦ የሰውን ልጅ ስጋና ደም ላልተገባ ተግባር ያውላል ተብሎ እንደተጻፈው ጭራቁ አብይ አህመድን የአማራን ሕዝብ ለማንበርከክ ብሎ በከፈተው ጦርነት የአማራን ልጅ ስጋና ደም እየተመገበ ያለ ሰው በላ መሆኑን ኢትዮጵያውያንም ሆነ ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ሊገነዘበው የሚገባ እውነት ነው። የአማራ ሕዝብ በማንኛውም የታሪክ አጋጣሚ በሀገሩ መሪና መንግሥት በዚህ ልክ የዘር ጭፍጨፋ ደርሶበት አያውቅም። ፋሽስቱ የጣልያን ወራሪ ክ1928 -33 ዓ.ም ካደረሰው በደል በማይወዳደር መልኩ በሕዝባችን ላይ በዚህ አምሳ ዓመት የደረሰበት በደል የላቀ ሲሆን የሀገር ልጅ በሆነው አብይ አህመድ የደረሰበት በደል ግን የሁሉ ቁንጮ ሆኖ በገሀድ የምናየው ጉዳይ ነው። የአማራን ሕዝብ ባሪያ አደርገዋለሁ ብሎ ቆርጦ የተነሳው አባገነን የገባበት ቅጀት ውስጥ ለመውጣት የሰላም ነጋሪት ቢጎሰምለትም መንቃት የሚፈልግ አይደለም።

ሰሞኑን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ)ን የጠቅላላ ጉባዔ ዓመታዊ ስብሰባን አደናቅፋለሁ ብሎ በማሰብ አመራሮቹ በሌሉበት በደቡብ ወሎ ዞን በአምባሰል ወረዳ በጀትና በድሮን የፈፀመው የንጹሓን ጭፍጨፋ የዚህ አይነተኛ ማሳያ ነው። አማራ መሆናቸውን የማያውቁ ሕጻናት በአብይ አህመድ የግል ንብረት በሆነው አየር ኃይል አማራ ተብለው ተጨፍጭፈዋል።

በእርግጥ የተሸነፈ ስነ ልቦና ባለቤት የሆነውና የስልጣን ጥሙ ከአካሉ የሚገዝፍበት - ከአዕምሮው የሚሰፋበት ይህ የዘመኑ የአፍሪካ አባገነኖች ቀንዲል ከምድር ጦር በዘለለ ሰው አልባ አውሮፕላንና ጀት የሚጠቀመው የሽንፈት ፅዋውን እየተጎነጨ ስለሆነ ነው። ኢትዮጵያዊው ኤዲ አሚን ዳዳ በሕዝባችን ላይ እየፈጸመ ያለው የዘር ጭፍጨፋ ሕዝባዊ ትግላችንን አይቀለብሰውም፤ የተከፈተብን መንግሥት መር ጦርነትም እንደሕዝብ መደራጀታችንን፣ መታጠቃችንን፣ አምባገነናዊ የብልፅግና ሥርዓትን ማስወገዳችንን አያስቀረውም። ሥርዓቱ በሕዝባችን ላይ የሚፈፅመው በደል ከማንኛውም ጊዜ በበለጠ የሚያበረታን እንጅ ክንዳችንን የሚያዝለው አይሆንም።

ስለሆነም ይህንን የአብይ አህመድን ሰይጣናዊ ተግባር ለመቀልበስ በቤተ አማራ (ወሎ) የምንገኝ ፋኖዎች በቀን 14/05/2017 ዓ.ም ወደ አንድነት መምጣታችን ይታወቃል። በመሆኑም ድርጅታችን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ) የመጀመሪያውን የጠቅላላ ጉባዔ ስብሰባውን በማድረግ በስኬት ያጠናቀቀ ሲሆን የማዕከላዊ ምክር ቤትንና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴውንም አዋቅሯል፤ በሥራ አስፈጻሚና በልዩ ልዩ መምሪያዎች ደረጃ የተመደቡ አመራሮችና ምደባውም የሚከተለውን ይመስላል።

1.ዋርካው ምሬ ወዳጆ --------ሰብሳቢ
2.አርበኛ ድርሳን ብርሃኔ ------ምክ/ሰብሳቢና ወታደራዊ አዛዥ
3.አርበኛ ሀብታሙ ደምሴ -----ምክ/ወታደራዊ አዛዥ
4.ኮሎኔል አባይ ባየው--------ወታደራዊ እቅድና ስትራቴጅ መምሪያ ኃላፊ
5. አርበኛ በለጠ ሸጋው ------ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
5.1. ኮሎኔል ፈንታው መኩዬ ----ምክትል ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
6.ሺ ዓለቃ ያረጋል አሰፋ-----ወታደራዊ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
6.1. አምሳ ዓለቃ ሲሳይ ገላነው---ምክትል ኃላፊ - ለሰው ሃብት አስተዳደር መምሪያ
6.2. ዶ/ር አቡበክር ሰይድ---ምክትል ኃላፊ - ለጤና ጉዳይ
7.መቶ አለቃ በሪሁን ደምሌ---ሎጂስቲክስ መምሪያ ኃላፊ
7.1.አርበኛ ሞላ ሰማው ------ምክትል ኃላፊ - ለስንቅና ትጥቅ ስርጭት
7.2. አርበኛ ኢሳይያስ መልኩ----ምክትል ኃላፊ - ለኦርዲናንስ ክፍል
7.3. አርበኛ ኑረዲን አበበ ----ምክትል ኃላፊ - ለትራንስፖርት ስምሪት
8.መቶ ዓለቃ ዮሴፍ አስማረ ---ወታደራዊ ሥልጠና መምሪያ ኃላፊ
8.1. አርበኛ ጌታቸው ሲሳይ ----ምክትል የሥልጠና መምሪያ ኃላፊ
9.አርበኛ ** ---ወታደራዊ መረጃ መምሪያ ኃላፊ
10. አምሳ ዓለቃ አደም አሊ ----ወታደራዊ ኢንዶክትሪኔሽን (ስርጸት) መምሪያ ኃላፊ
10.1.አርበኛ ሙላት አላምረው-----ወታደራዊ ኢንዶክትሪኔሽን መምሪያ ምክ/ኃላፊ
10.2.አርበኛ ተመስገን በቀለ ----የኪነትና መዝናኛ ክፍል ኃላፊ
11.አርበኛ ተሾመ ፈንታዬ -----ልዩ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ
12.ኮሎኔል ሞገስ ዘገዬ -----ወታደራዊ አማካሪ
13.አርበኛ ሄኖክ አዲሴ ----ምክ/ሰብሳቢና የፖለቲካ ጉዳዮች ጽ/ቤት ኃላፊ
14.አርበኛ ሞገስ አበራው ----የፖለቲካ ጉዳዮች ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ
15.አርበኛ አራጋው ያለው-----የስትራቴጅክ ጉዳዮች መምሪያ
15.1.አርበኛ ፍቅር መንግስቱ----የስትራቴጅክ ጉዳዮች መምሪያ ምክ/ኃላፊ
16.አርበኛ ሽመልስ ትዛዙ -----የውጭ ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ
16.1.አርበኛ አብደላ አያሌው -----የውጭ ጉዳይ መምሪያ ምክትል ኃላፊ
17.

Ethio 251 Media

15 Feb, 09:57


አርበኛ አበበ ቀዬ -----የአደረጃጀት መምሪያ ኃላፊ
17.1.አርበኛ አሰፋ መሰለ -----የአደረጃጀት መምሪያ ምክትል ኃላፊ
18.አርበኛ አበበ ፈንታው ----የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ
18.1.አርበኛ ናትናኤል አክሊሉ ---የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ምክ/ኃላፊ
18.2.አርበኛ ምኒልክ ፈንታሁን --ሚዲያና ኮሚኒኬሸን ኃላፊ
19.አርበኛ ዚነት አደም-----የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ
19.1.አርበኛ አበበች ሲሳይ---የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ምክ/ኃላፊ
20.አርበኛ ደስታው መለሰ -------የጽ/ቤት ኃላፊ
20.1.አርበኛ አለባቸው ቀስቅሴ --ምክትል የጽ/ቤት ኃላፊ
21.አርበኛ ንጉስ አዳነ ----የፋይናንስና ግዥ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
21.1.አርበኛ አማረ አያሌው --የፋይናንስና ግዥ አስተዳደር መምሪያ ምክ/ኃላፊ
22.አርበኛ ረዳ ውበቱ ----------የሐብት አፈላላጊ መምሪያ ኃላፊ
23.አርበኛ እስራኤል እሸቴ ---የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ
23.1.አርበኛ ፍቅሩ ፈንታ---የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ምክ/ኃላፊ
24.አርበኛ አክሎግ ሲሳይ-------የእቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊ
25.አርበኛ ****************-የመረጃና ደህንነት መምሪያ ኃላፊ
25.1.አርበኛ *************-ምክ/የመረጃና ደህንነት መምሪያ ኃላፊ መሆናቸውን ለሰራዊታችንና የኅልውና ትግላችንን በስስት ለሚመለከተው በአገር ውስጥና በውጭው ዓለም ለሚኖረው ሕዝባችን መግለጽ እንወዳለን።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ለትግሉ ደጋፊዎች በሙሉ፣ ለአማራ ሕዝብ፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብና ለሥራዓቱ ደጋፊዎች የሚከተለውን መልዕክት ማስተላለፍ እንወዳለን!

1. የበሰበሰውን የብልጽግና ሥርዓት በመደገፍ ወይም የሥርዓቱ አመራር በመሆን እያገለገላችሁ ያላችሁ አካላት፣ በብልጽግና መንግሥት መከላከያ ሰራዊትና የፖሊስ ተቋማት ያላችሁ መሪዎችና የሰራዊት አዛዦች ብዙ የሥራ ባልደረቦቻችሁ እንዳደረጉት የአማራን ሕዝብ የኅልውና ትግል እንድትቀላቀሉ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ) ጥሪ ያቀርብላችኋል፡

2. ውዱ የአማራ ሕዝብ - የሥርዓቱ ሕይወት የሆነውን መንግሥታዊ መዋቅር በማፈራረስ፣ የሥርዓቱ ጠባቂ የሆነውን የብርሃኑ ጁላን ሰራዊት በማግለል ከትጥቅ ትግልህ ጎን ለጎን በሁሉም ከተሞቻችን በሕዝባዊ ማዕበል ስርዓቱን ለመገርሰስ ዝግጁ እንድትሆን እናሳስብሃለን።

3. ውድ ኢትዮጵያዊያን - አብይ አህመድ ሁሉም አባገነኖች እንደሚያልፉት በቅርብ ቀን ያልፋል! የማያልፉት ኢትዮጵያዊያንና ኢትዮጵያ ናቸው! የአማራን ሕዝብ የኢትዮጵያ አካል ነው ብሎ የሚያምን ኢትዮጵያዊ ሁሉ ፋሽስቱን አብይ አህመድንና የገማውን ሥርዓቱን እንዲቃወምና ከአማራ ሕዝብ ጎን እንዲሰለፍ በአማራ ሕዝብ ስም የትግል ጥሪ እናቀርባለን።

4. በውጭው ዓለም የምትኖሩ ወገኖቻችን የሥርዓቱን ሁለንተና ለመገርሰስና ከሕዝባችን ጫንቃ ላይ ለአንዴና መጨረሻ ጊዜ አውርዶ ለመጣል የምናደርገውን ትግል በገንዘብ እንድትደግፉ፣ የዘር ጭፍጨፋውን በዲፕሎማሲና በአደባባይ ሰልፎች ለዓለም መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተቋማትና ለዓለም አቀፉ ማህበርሰብ ደጋግማችሁ እንድታጋልጡ እናሳስባለን።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን
አማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አማራ)
ወሎ፣ አማራ፣ ኢትዮጵያ፤

Ethio 251 Media

14 Feb, 17:38


የዛሬ የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-

https://twitter.com/i/broadcasts/1lPKqMrLlgMKb

https://rumble.com/v6ksuha--251-zare-february-14-2025-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

14 Feb, 17:20


#የአፈና_መረጃ_ቲሊሊ
ወንበዴው መንግስታዊው ቡድን ነገ ማለትም 8/6/2017 ጀምሮ የከተማዉን ወጣት በማፈን አስገድዶ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ካምፕ ለማጋዝ ዝግጅት ጨርሰዋል። ስለሆነዉ ሁሉም የከተማው ህዝብ እራሱን እንዲጠብቅ መልክታችን ነው።
የአማራ ፍኖ በጎጃም ጎጃም አገው ምድር ክፍለ ጦር ዘንገና ብርጌድ ቲሊሊ!!

Ethio 251 Media

14 Feb, 16:07


ሰበር  የድል ዜና
   በሸዋ ክፍለ ሃገር መርሀቤቴ አውራጃ ፌጥራ ከተማ ላይ አገዛዙን በመንገድ መሪነት እና በተላላኪነት ሲያገለግል የነበረ ስሙ ንጉሴ ጌታነህ የተባለ ባንዳ ቀንደኛ ሚሊሻ በአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር መቅደላ ብርጌድ አናብስቶች ተቀንድሿል።
  ይህ ሚሊሻ ህዝባችንን ሲዘርፍ  ሲመዘብር ሲደበድብ በተለይ የአገኘውን ወጣት ሁሉ እናንተ ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ በሚል በአፈሙዝና በሰዴፍ ሲደበድብና ሲያቆስል የነበረ ፣ለጠላት የብልፅግና ሰራዊት መንገድ በመምራት የሚታወቅ ሲሆን በተደጋጋሚ የአታርፍምወይ የሚል ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውም ማስጠንቀቂያችንን ሊቀበል ባለመቻሉ ዛሬ የካቲት 07/2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ገደማ  በፌጥራ ከተማ የተለመደ ተግባሩን እየፈፀመ ባለበት አይበገሬወቹ የፋኖ ሃይሎች ልዩ ክትትል በማድረግ መሃል መንገድ ላይ በአንድ ጥይት ቀልበው አሰናብተውታል።ይዞት የነበረውም መሳሪያ ገቢ ሆኗል።
    አሁንም ከስርአቱ ጋር ወግናችሁ የባንዳነት ተግባር ላይ የተሰማራችሁ የታሪክ አተላወች ከእኩይ ተግባራችሁ ተቆጥባችሁ የህልውና ትግል ለሚታገለው ፋኖ  ጋር እጃችሁን ስጡ ክፍ እያልን  የተሰጣችሁን ዕድል ካልተጠቀማችሁ በአገኘነው አጋጣሚ ሁሉ በፈእርምጃ እንደምንወስድ ይህ እጣ ፈንታና መሰል እንደሚደርሳችሁ ለማሳሰብ እንወዳለን።
                          ክብር ለተሰውት ሰማዕታት
                          ድላችን በተባበረ ክንዳችን
       ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ
የካቲት 07/2017ዓ.ም
✍️ከአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል

Ethio 251 Media

14 Feb, 12:17


የአማራ ፋኖ በወሎ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ከሆነው ፋኖ በለጠ ሸጋው ጋር የተደረገ ቆይታ

Ethio 251 Media

14 Feb, 11:59


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳምነው ኮር ተፈራ ማሞ ክፍለጦር በላስታ ቅዱስ ላልይበላ ከተማ ላይ አስደናቂ ጀብዱ ሰራች።

የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳምነው ኮር ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ሻምበል ሀብታሙ ሻለቃ የካቲት 06/2017ዓ.ም ከሌሊቱ 6:00 እስከ 7:00 ሰዓት በላስታ ቅ/ላልይበላ ከተማ ላይ አስደናቂ ጀብዱ ሰራች።

በባለምጡቅ አዕምሮ የጦር ጠበብቶች የሚመራው  በአንድ አይን ጥቅሻ የሚግባባዉ  በላስታ አሳምነው ኮር ስር  የተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር  ሻምበል ሀብታሙ ሻለቃ የተለያዩ የውጊያ ስልቶችን  እንደ ቤተ-ሙከራ እየቀያየረ በአፓርታይዱ የብርሀኑ ጁላ ጦር እንዲሁም  በጥቁር አማራ ሚሊሻ እና አድማ ብተና  ላይ በላስታ ቅ/ላልይበላ ከተማ ልዩ ስሙ ሽምብርማ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ከሌሊቱ 6:00 እስከ 7:00 ሰዓት ላይ ለአንድ ሰዓት በወሰደ  የሌሊትና የከተማ  ኦፕሬሽን ከሻለቃዋ በተውጣጡ  በትንሽ የሰው ሃይል  የአገዛዙ ጦር ይዞት የነበረውን ምሽግ በማስለቀቅና ሻለቃዋ  ባደረገችው ተጋድሎ  እግሬ አውጭኝ ብሎ ፈርጥጦ የተመታ ተመቶ ፋኖ በፈለገው ጊዜ ሠዓትና ቀን ማንኛውንም አይነት ኦኘሬሽን ማድረግ እንደሚችል በጠላት ጦር ላይ ከባድ የስነ ልቦና ጫናና የሞራል ውድቀት  እንዲሁም ታላቅ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳምነው ኮር ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር ሻምበል ሀብታሙ ሻለቃ ታላቅ ጀብዱ ፈፅማለች።

ድንጋጤን የፈጠረ በፋኖ ሰራዊት  ዘንድ  ደምን የሚያሞቅ ወኔን የሚያስትጥቅ ጀብዱ ሆኗል።

በዚህ ምት የተበሳጨዉ የብርሃኑ ጁላ አፓርታይድ ስርዓት  ጦር ድንጋዩም ዛፉም ፋኖ እየመሰለው ሲርበተበት እስከ ንጋት ድረስ የእውር ድንብሱን ሲተኩስ እንዳደረ እና ወጣቶችን ሴቶችን አዛውንቶች በሙሉ እየደበደበ እያንገላታና እያሰረ መሆኑን የመረጃ ምንጮቻችን አድርሰውናል።

ድል ለመላው አማራ ፋኖ!     
የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

Ethio 251 Media

14 Feb, 10:06


🔥🔥 ይድረስ ለባህርዳር ህዝብ 🔥 🔥
የጥንቃቄ መልክት ስለማስተላለፍ

አሁን ላይ አጋጣሚወችን በመጠቀም በርካታ ግለሰቦች ከመንግስት ጋር በመሆን በመተባበር በፋኖስም በደብዳቤ እና በስልክ የተለያዩ በመደወል በማስፈራራት እና ሰወችን በማገት ያልተገባ ገንዘብ የመሰብሰብ ስራ እየተሰራ ነው የባህርዳር ባለሀብቶችን የተለያዩ ድርጅቶችን ተቋማትን ባለሙያወችን እያንገላቱ በመውሰድ ፋኖን ከህዝብ ለመነጠል በጤና መድን እና በኮሪደር ልማት ስም እና የአማራ ባለሀብቶችን በማሸማቀቅ በማማረር ከክልሉ እንዲወጡ ለማድረግ መንግስት የተለያዩ ዘዴወችን በመጠቀም አቅዶ እየሰራ በመሆኑ መላው በባህርዳር ከተማ ውስጥ በተለያዩ ከትንንሽ እስከ ትልልቅ ድርጅት እና ተቋማት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ክልሉን በማልማት ላይ ያላቹህ አሁን ላይ እየተከናወነ ያለውን አስነዋሪ ተግባር የፋኖን ስነ ምግባር ያልተላበሰ በመሆኑ በየትኛውም አደረጃጀት ውስጥ ያለ ፋኖ ፈፅሞ የሚቃወም የማይደግፍ መሆኑን በመረዳት እያንዳንድን ህገወጥ ተግባር በፋኖ ስም ገንዘብ የሚሰበስቡትን እና እገታ የሚሰሩትን ትክክለኛ ማንነት የሚገልፅ በፎቶ የተደገፈ ማስረጃ እንድታደርሱን እያልን በእነዚህ ስግብግብ ግለሰቦች እና ቡድኖችን በመከታተል የመጨረሻ የማያዳግም እርምጃ የምንወስድ መሆኑን እንገልፃለን።

የአማራ ፋኖ በጎጃም 1ኛ ክ/ጦር ባህርዳር ብርግድ እና የሻለቃ አንሙት ያዛቸው ብርጌድ በጋራ መልክታችን እናስተላልፋለን።

ሐብታሙ የሱፍ አማረ ጌታቸው
የባ/ዳር ብርጌድ የሻለቃ አንሙት ያዛቸው ብርጌድ ብርጌድ
ቃል አቀባይ ቃል አቀባይ

ትግላችን አይሸጥም አይለወጥም

💚 ድል ለአማራ ህዝብ 💛❤️
ድል ለአማራ ፋኖ
የካቲት 06-06-2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

14 Feb, 10:04


🔥ሰበር ዜና
የአማራ ፋኖ በጎጃም የራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም/5ኛ ክ/ጦር/ ሽንዲ ከተማ ላይ የተሳካ ኦፕሬሽን አካሂዷል።ይህንን የተሳካ ኦፕሬሽን የመሩት የክፍለ ጦሩ ጦር አዛዥ መቶ አለቃ ገረመው አጋዥ ፣የክፍለ ጦሩ ም/ዘመቻ መሪ 50 አለቃ መኳንት እንዲሁም የብርጌድ አዛዥ እና የሻለቃ አዛዥ በጋራ በመሆን የመሩት ሲሆን ክ/ጦሩ የሚመራቸውን ብርጌዶች በማቀናጀት ማለትም ጓጉሳ ብርጌድ፣ወርቅ አባይ ብርጌድ፣ወምበርማ ብርጌድ፣5ኛ ክ/ጦር ተወርዋሪወች፣ዳጃች አስቦ ቡሬ ዳሞት ብርጌድ አባል ከሆኑት ሁለት ሻለቃወች ውስጥ ዘመነ ሻለቃ እና አባይ ሻለቃ እንዲሁም በፋኖ ሀብታም የሚመራው የወለጋ ፋኖ በጋራ በመሆን ሽንዲ ከተማ ላይ ከበባ በመስራት አይ*ቀጡ ቅጣት በመቅጣት ጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አስመዝግበዋል።

በዚህ አውደ ውጊያ 94 ሙ*ት እና ቁጥር ስፍር የሌለው ቁ*ስለኛ የሆነ ሲሆን የሽንዲ ከተማ የግል እና የመንግስት ጤና ጣቢያወች በቁ*ስለኛ ተጨናንቀዋል ሲሉ ምንጮቻችን ገልፀውልናል።ከዚህ በተጨመሪ ከጠላ*ት ቁጥሩ የማይታወክ ተተኳሽ ፣ 6 ክላሽንኮፍ መሳሪያ፣ ሁለት የስርአቱ አገልጋይ ሚኒሻ ተማርኳል።

በተጨማሪም አሳዛኝ የሚያደርገው የብልፅግና መንግስት የራሱን አገልጋይ ሚኒሻና፣ ፖሊስ እና አድማ ብተና ሲሞቱ አስከሬናቸውን ሳይቀብር ለይቶ የመከላከያ አስ*ከሬን በመቀብር አማራ ጠል*ነቱን በግልፅ አሳይቷል።በአጠቃይ ጠላ*ት የደረሰበት ከፍተኛ ም*ት በኮረኔል ምስራቅ የሚራው ክ/ጦር በመፈራረሱ ምክነያት ተጨመሪ ሀይል ከኮሶበር ሌላ ክ/ጦር ጨምሯል ሲሉ የውስጥ ምጮች ገልፀውልናል።


አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!
የአፋጎ 5ኛ ክ/ጦር የሚዲያ ባለሙያ ፋኖ ዮሴፍ ሀረገወይን

Ethio 251 Media

13 Feb, 18:36


የኦሮሙማው ፋሽስታዊ አገዛዝና ራሱን መከላከያ እያለ የሚጠራው ጅምላ ጨፍጫፊው የዓብይ ወራሪ ሠራዊት በአሁኑ ሰዓት በሰላም ማስከበር ሰበብ በአማራ ሕዝብ ያልፈጸመው ግፍና በደል የለም።

በዓለም ዓቀፍ የጦር ወንጀል የሚያስጠይቁትን ለምሳሌ ተቋማትን ማውደም፣ህጻናትን መጨፍጨፍ፣ ንጹሐንን መግደልና ማገት፣ ሴቶችን መድፈር፣ የዜጎችን ንብረት መዝረፍና ወዘተ የመሳሰሉትን የጦር ወንጀሎችን እየፈጸመ ያለ የሽብር ቡድን ነው።

ከሰሞኑም በደብረ ኤልያስ የሚገኘው ወራሪ ሠራዊት ዜጎች በሰላም ወጥተው በሰላም እንዳይገቡ ዝርፊያውን ቀጥሎበታል።

በደብረ ኤልያስ ከተማ ዙሪያ በሁሉም ቀሮች ዘራፊ ቡድኑን በማሰማራት በጤና መድኀን ሰበብ ገቢያ የመጣውን አርሶ አደሩን እየዘረፉ ሲያስለቅሱት ሰንብተዋል።በትናንትናው እለት ማለትም በየካቲት 05/2017 ዓ.ም በደብረ ኤልያስ ወረዳ የቀጋት ቀበሌ የፉይ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሚካኤል ማሕበረሰተኞች ብር አዋጥተው የጋራ ልብስ ሊገዙ ገቢያ በሄዱበት የያዛችሁት የጤና መድኅን ብር ነው በማለት 95000 ዘጠና አምስት ሽህ ብር ዘርፎ ወስዶባቸዋል።

ብልጽግና ባሁኑ ሰዓት በጤና መድኅን ስም የአማራ ሕዝብን ለመጨፍጨፍ የሚረዳውን የጦር መሳርያ ለመግዛትና ለጥፋት ሠራዊቱ ደሞዝ እንዲሆን የማህበረሰቡን ገንዘብ እየዘረፈ መሆኑ ተረጋግጧል።

ድል ለሕዝባችን!
ክብር ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ(ትውልድ፣ተስፋ፣አስተሳሰብ)
ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው

የካቲት06/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

13 Feb, 17:07


251 ዛሬ

Twitter (X)
https://x.com/251media/status/1890083352113221738?s=46

Rumble👇
https://rumble.com/v6kdvjm--251-zare-february-13-2025-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

13 Feb, 12:56


ሰበር ዜና!

"የደሴና የኮምቦልቻ ሕዝብ ምሽት ከ12 ሰዓት በኋላ ከቤት ባለመውጣት ይተባበረን" አርበኛ በለጠ ሸጋው

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) በአንባሳል ሰንሰላታማ ተራራ አስናደቂ ጀብዱ መፈጠሙን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በለጠ ሸጋው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

አገዛዙ የፋኖን ጉባኤ ለመበተን በሆዱ በወደቀውና የአብይ አህመድ የግል ጄነራል በሆነው በሌ/ጄነራል አሰፋ ቸኳል የሚመራው ሰሜን ምስራቅ ዕዝ በምድር 46ኛ እና 47ኛ ክፍለጦር በኩታበር አቅጣጫ፣ ከዚህ በፊት ከድምሰሳ የተረፉና ሚኒሻ፣ አድማ ብተና እና ፖሊስ የተሟላላቸው 48ኛ እና 49ኛ ክፍፉጦርን በማርዬ በኩል በአየር ደግሞ ሚግ እና ዙ-23 አሰልፎ ቢመጣም የነብዩ አሳምነው ጽጌ ልጆች በደቡብ ወሎ ዞን አንባሰል ሰንሰለታማ ተራሮች ድባቅ መተነዋል ሲል አርበኛ በለጠ ሸጋው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተናግሯል።

ይህ ውጊያ ትናንት ጧት የጀመረ ሲሆን አሁንም እንደቀጠለ ቢሆንም 2 ብሬን፣ 2 ስናይፐር እና ከ50 በላይ የተቆጠረ ክላሽንኮቭ መሳሪያ ከበርካታ ተተኳሽ ጋር ገቢ ሁኗል፣ ከ50 በላይ የብልጽግና ሰራዊት ተማርኳል፤ ቀሪው ደግሞ በአንባሰል ሰንሰላታማ ተራሮች ገደል የገባ ሲሆን ውጊያ ላይ ስለሆን ይህ መረጃ ጥቂት ነው።

አገዛዙ ይሄን ውጊያ ለመቀልበስ 5 ድሮን እና 2 ጊዜ የሚግ ጥቃት በንጹሃን ላይ ፈጽሟል፤ በዚህ ጥቃት ከአንድ ቤተሰብ 6 ንጹሃን፣ አንዲት እና ከእነ አዘለቻት ህጻን ሲገደሉ የሰባ አመት አዛውንት ቆስለው በፋኖ የሕክምና ቡድን ሕክምና እየተደረገላቸው መሆኑን የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ በለጠ ሸጋው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ውጊያው አሁንም እንደቀጠለ ነው፤ የደሴና ኮምቦልቻ አካባቢው ማህበረሰብ ከወትሮው በተለዬ ልዩ ጥንቃቄ እንዲያደርግና በተለይ ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ልዩ ጥንቃቄ እንዲያደርግ አርበኛ በለጠ ሸጋው ጥሪ አቅርቧል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

Ethio 251 Media

13 Feb, 06:26


የአብይ አህመድና የነ ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ነውር!

የአብይ አህመድ መራሹ የብልፅግናው ስርአት ለእድሜ ማራዘሚያነት ሲል ያቋቋመው የምክክር ኮሚሽን ብሎ የሚጠራው እና የአገዛዙ ካድሬወች ማህበረሰቡን በግዴታ ትሄዳለህ/ሽ በማለት የተመቸውን እየመረጠ ለስብሰባ(ለምክክር)በሚል በወታደሮቹ እያስፈራራና እየደበደበ ከመርሀቤቴ ወደ አዲስ አበባ ይዟቸው ከሄዱት ውስጥ ከ 20 (ሃያ)በላይ የሚሆኑት በአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር ተይዘው የተለያየ ምርመራ ከተደረገባቸው በኋላ የተሃድሶ ስልጠና ተሰጡ።

በቁጥጥር ስር ውለው ከነበሩት ውስጥ ከተለያየ የማህበረሰብ ክፍል ማለትም ከሃገር ሽማግሌ፣ከእድር ዳኛ፣ከሃይማኖት አባቶች እና ሌሎችም የተውጣጡ መሆናቸውን ገልፀው የአገዛዙ ሃይሎች በማፈስ በመስፈራርቾ ምንም አታመጡም በሚል ዛቻ በግዳጅ መሄዳቸውንም አስረድተዋል።

በስሙ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን ተብሎ የተሰየመው ቡድን ራሱ አምባገነኑ የብልፅግናው ስርአት ለወንበሩ ማቆያ ሲል የወለደው እንደሆነና የአማራን ህዝብ ጥያቄ ለመመለስና ህልውናውን ለማስጠበቅ የሚያስችል ቁመናም እንደሌለው አብራርተዋል።

በማጠቃለያም የክፍለ ጦሩ ወታደራዊና ፖለቲካዊ አመራሮች የትግሉን አሁናዊ ሁኔታና ቀጣይ ጉዞ እንዲሁም አሁን የሄዱበት መንገድ የተሳሳተ መሆኑን በማስረዳትና አመክሮ በመስጠት እንዲሁም የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት እንዲለቀቁ ተደርጓል።

ክብር ለተሰውት ሰማዕታት
ድላችን በተባበረ ክንዳችን
የካቲት06/2017 ዓ.ም
ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ
✍️የአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል

Ethio 251 Media

13 Feb, 05:54


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ያለፈውን ሁለት ዓመት የትግል ሂደት በመገምገም የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎችን ድርጅቱ በመስጠት ጉባኤውን በስኬት አጠናቀቀ።

ጉባኤው በወሎ ቤተ-አምሓራ ሰንሰላታማ ተራራ ላይ የተካሄደ ሲሆን ከመርጦ ዲክላሬሽን በመቀጠል ስኬታማ እንደሆነ የድርጅቱ አመራሮች የገለጹ ሲሆን በዚህ ጉባኤ ላይ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች፣ የኮር አመራሮችና የ25ቱም የክፍለጦር ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በውይይቱም ባለፉት ሁለት ዓመት ትግል እየተደረገ ስላለው የአማራ የህልውና ትግል፣ ስለቀጠናው የኃይል አሰላለፍ፣ ስለድርጅታችን የቀጣይ የአጭር ጊዜና የረዥም ጊዜ ሥራዎች እና ሌሎችም ጥብቅ ጉዳዮች ተነስተው የጋራ አቋም በመያዝ ተጠናቋል።

ይህ ውይይት እየተካሄደ ባለበት ወቅት አገዛዙ የአየር ኃይሉንም እግረኛ ኃይሉንም ያሰለፈ ቢሆንም ከኮምቦልቻ በ30 ኪሎ ሜትር ርቀት የምትገኘውን ከተማ የተቆጣጠርን ሲሆን በተንታ፣ በምዕራብ ወሎ ሳይንት ቀጠና፣ በላስታ፣ በአምባሰል እና በሌሎች ቀጠናዎች ከፍተኛ ተጋድሎ ተደርጎ በርካታ ድሎችን አስመዝግበናል፣ ይህ ተጋድሎም ተጠናክሮ ይቀጥላል።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

12 Feb, 19:02


https://rumble.com/v6k0cc1--ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

12 Feb, 17:31


የዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-
https://rumble.com/v6jz6d7--251-zare-february-12-2025-ethio-251-media.html

https://twitter.com/i/broadcasts/1PlKQMRkzOzKE

Ethio 251 Media

12 Feb, 17:24


ደንደገብ_ባሶሊበን!

ዛሬ በ05/06/2017ዓ/ም የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ከጥዋቱ 1:00 ከበባ በማድርግ በሶሊበን ወረዳ በደንደገብ ቀበሌ ልዮ ስሙ ከብዳም ጎጥ ከአቶ ገድፈውን ቤት ከ70 በላይ ኩንታል ስንዴ ጭኖ ወስዷል::

አቶ ገደፍው የባሶ ሊበን ወረዳ የደንደገብ ቀበሌ ጊዜያዊ አስተዳደር ሲሆን ከትግል ማንም አያቆመኝም በማለት የአማራ ፋኖ በጎጃም የሀሐዲስ አለማሁ ክ/ጦር  የአብራጅት ብርጌድ ጋር በመሆን ስርዓቱን እታገላለሁ ብሏል:: ከጠላት ያበራችሁ በተለይ ሚሊሻ አዳም ብተና እና ፓሊስ የፋኖን በትር መቋቋሞ ሲያቅታችሁ ዝራፊያ የማያወጣ እንደሆነ  ብትረድ ጥሩ መሆኑን እያሳወቅን አደብ ያዙ እንላለን:: ለፈፀማችሁት አስነዋሪ ተግባር ነገ  እንጠያየቃለን!      
           
©አብራጅት ብርጌድ!!!!

Ethio 251 Media

12 Feb, 16:46


ሰበር ዜና!
ቦካክሳ ከተማን በፋኖ ተያዘች!

የአማራ ፋኖ በወሎ /ቤተ-አማሓራ/ የምስራቅ አማራ ኮር 1 በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የሚመራው ባለሽርጡ ክፍለጦር እና ልጅ እያሱ ኮር ራስ አሊ ክፍለ ጦር 1ኛ ሻለቃ የደቡብ ወሎ ዞን ቦከክሳ ከተማን ታላቅ ጀብድ በመፈፀም ከወራሪውና ከዘራፊው ስርዓት ነፃ በማውጣት ተቆጣጠሩ፡፡

በተደረገው ተጋድሎ የስርዓቱ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት እንዲሁም ሆድ አደር ሚሊሻና አድማ ብተና ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል፡፡

በዚህም ከሞት የተረፈው የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት ከቦከክሳ ወደ ቢስቲማ እየፈረጠጠ ይገኛል፡፡

በዛሬው የህልውና ተጋድሎ 18 የዙፋን ጠባቂው ኃይል እስከወዲያኛው ሲደመሰስ 10 የሚሆነውን ኃይል ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም ተጋድሎ 1500 የክላሽ ተተኳሽ እስከ ነፍስ ወከፍ መሳሪያ መመረክ ተችሏል።

የጀግኖቹን በትር መቋቋም ያቃተዉ የባንዳ ጥርቅም የግለሰብን ሀብትና ንብረት እየዘረፈ፣ እያወደመ እና የዘወትር ልምዱ የሆነዉን በንፁሀን ላይ በርካታ ግፎችን እየፈፀመ፣ የግለስብ ቤቶችን እያቃጠለ ፈርጥጧል፡፡

ይህን አመርቂ ድል እንድንጎናፀፍ ያደረገን አስቻይ ሁኔታ ደግሞ በቅርቡ የተመሰረተው የአማራ ፋኖ በወሎ /ቤተ-አማሓራ/ አንድነት ነው፡፡ ይሄን የሰሩና ይህ እንዲሆን ለተጉ የድርጅታችን አመራሮች ከልብ እናመሰግናለን።

"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"

ፋኖ መምህር መሀመድ ሞገስ
የአማራ ፋኖ በወሎ /ቤተ-አማሓራ/ የምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ

የአማራ ፋኖ በወሎ/ቤተ-አማሓራ/
የካቲት 05/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

12 Feb, 15:47


https://youtu.be/s_cAAFJMNk8?si=a21XIAzGveoHgURY

Ethio 251 Media

12 Feb, 10:59


⚡️▶️#መረጃ: የአማራ ማህበር በአሜሪካ (AAA), የሚከተለውን ልዩ ክሊፕ ለሁሉም የማህበሩ ድጋፍ ሰጪዎች ሊያደርስ ይወዳል። ይህ ክሊፕ እ.ኤ.አ. በ2024 በአማራው ላይ በኢትዮጵያ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት ለማስቆም እንዲሁም የጥቃቱ ፈጻሚ ወንጀለኞችን ተጠያቂ ከማድረግ አንጻር በማህበሩ የተሰሩ የሚዲያ፣ የሰብአዊ መብት ረገጣዎችን ማስመዝገብ እና የመንግስት ግንኙነቶች ስራዎችን የሚያካትት ነው።

https://youtu.be/0uyUOS6q5EM

Ethio 251 Media

11 Feb, 18:30


https://twitter.com/i/broadcasts/1DXxyqgQlAgxM

Ethio 251 Media

11 Feb, 14:15


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለጦር  ነበልባል ብርጌድ ታሪካዊ የሚባል ድል ተቀናጅቷል።

ከዛሬ አራት ቀን በፊት በወራዋ የካቲት መግቢያ በቀን 1/6/2017ዓ.ም ከሞጆ መስመር እሬሽን ጭኖ የመጣው ወንበዴው የአብይ የግል ሰራዊት ስመ መከላከያ በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ቦሎ ጊዮርጊስ መሽጎ የነበረውን አረመኔ ሰራዊት በአጃቢነት ቀንታ ወደ በረኸት ወረዳ በረሃውን አቋርጦ ከሰም ጅረቱን አልፎ ሲግበሰበስ ባለታሪኮቹ በሃምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን ከልክሌ ዋና ጦር አዛዥነት የሚመሩት ከመብረቅ ብልጭታ የሚፈጥኑት ነበልባሎቹ ከሰም ድልድይን ጠላት እንደተሻገረ ገልደሚያ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ግትልትሉን የአብይን ወታደር በፈፀሙበት መብረቃዊ ጥቃት ሰባቱን በጥቁር አስፓልት ከምድር ቀላቅለውት ጠላትን በማበራዬት ጀባ አሉት።

ነበልባሎቹ ያዋከቡትን የአብይ ግብስብስ ሰራዊት በመቶ አለቃ ይላቅ ብርሃነ ዋና ጦር አዛዥነት የሚመራው የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለ ጦር ተስፋ ብርጌድ ሀይለማርያም ብርጌድ ነበልባል ብርጌድ በተናበበ መንገድ በየመንገዱ ደፈጣ በማድረግ ከአረርቲ ወደ በረኸት መተህ ብላ የሚጓዘውን አፋሽ ሰራዊት እየተቀባበሉ ለአራት ቀን ወንበዴው የሚተኩሰውን ከባድ መሳሪያ ዙ-23 ሞርተር ጀነራል መድፍ ቢኤም በገፍ ቢተኩስም የሸዋ ፈርጦቹ ጠላትን ያሠበበት ሳይደርስ በገፍ ሙትና ቁስለኛ አድርገውት ያበራዩት እንደሆነ እና ጠላት በደረሰበት ሽንፈት በበረኸት ወረዳ የንፁሃን ቤትና ንብረት አቃጥሎ የተረፈው የጠላት ሀይል ወደ አረርቲ ከተማ ፊቱን አዙሮ በዛሬው እለት4/6/2017ዓ.ም ሲፈረጥጥ የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለ ጦር ነበልባል ብርጌድ በየቦታው በጣሉት ደፈጣ ከጠዋት ጀምረው የብርጌዱ ቃኚና መሃንዲስ ተወርዋሪ ፋኖች በበረኸት ወረዳ ቆስጤ ገብረኤል እና ምንታምር ቀበሌ መሀከል በከፈቱበት መብረቃዊ ጥቃት የአገዛዙ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኖ በደረሰበት ጥቃት ተደናግጦ በየአቅጣጫው ተበታትኖ ወደ ከሰም አስፓልት ተከትሎ ሲፈረጥጥ ከቆስጤ በታች ደፈጣ የያዙት ሌላኛዎቹ ቀጫጭኖቹ የነበልባል ፋኖ በመክት የሚመሩት ሺአለቃ ሁለት አንድ ሻንበል አገዛዙን የመሣሪያ ቃታቸውን በመፈልቀቅ ምላጫቸውን እየነካኩ ጠላትን እየቀነደሹ አስፓልቱን ሙሉ ሙትና ቁስለኛ አድረገውት  መስመር ሲለቁለት ተናባቢዎቹ በፍቅር የተሞሉት ነበልባሎች በፋኖ ቸሩ የሚመሩት ሺአለቃ አራት አንድ ጋንታ ከሰም ድልድይ በየመንገዱ ሲመቱ  ተርፈው ወደ አረርቲ ከተማተ የሚፈረጥጠውን የአብቹ ሰራዊት የጥይት ሀሩር በከሰም በረሃ አፈሰሱበትተ የአብቹ ሠራዊት በበረሃው ውሃ ውሃ እያለ በነበልባሎቹ ጥይት እየተጋተ ሙት በሙት ሆነው የተረፈው ወደ አረርቲ የፈረጠጠ መሆኑን የአማራ ፋኖ በሸዋተ ከሰም ክፍለ ጦር የነበልባል ብርጌድ ፋኖ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ኢንጂነር ታደሠ ወንድሙ አሳውቀዋል።

    ድል ለአማራ ፋኖ!!!
  አዲስ ተስፋ !!!
አዲስ አዲስ ትውልድ!!!
  
ዘላለማዊ ክብር ስለነፃነት ለተሰው ሰማዕታት።

መረጃው/ የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለ ጦር የነበልባል ብርጌድ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ነው።
   
        የካቲት 4/6/2017ዓ.ም

         

Ethio 251 Media

11 Feb, 14:03


ውይይትና ድርድርን በተመለከተ የዐማራ ዲያስፖራ ዓለም ዓቀፍ ፎረም የአቋም መግለጫ!

የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም.

ሰሞኑን በተለያዩ መድረኮች ላይ እንደተገለጸው፣ አንዳንድ የፋኖ ቡድኖች፤ ከአፍሪካ ኅብረት፣ ከአውሮፓ ኅብረት፣ ከኢጋድ
(IGAD)፣ እና ከአሜሪካ መንግሥት ተወካዮች ጋር በወሎ ዳውንት ውስጥ ግንኙነት አድርገው እንደነበር ለመረዳት
ተችሏል። ግንኙነቱም ድርድር ወይም የድርድር ቅድመ-ዝግጅት ይሆናል በሚል ግንዛቤ ከተለያዩ አቅጣጫዎችም ስጋት
ተገልጿል።

ለዚህም ፍራቻ እንደ ተጨማሪ ጠቋሚነት የሚቀርበው፣ በግንኙነቱ የአፍሪካ ኅብረትና ኢጋድ ተወካዮች ተሳታፊ መሆናቸው ነው:: ሆኖም፣ ግንኙነቱን ያደረገው ቡድን መሪዎች በዲፕሎማሲና ሰብዓዊ ጉዳዮች ላይ የተደረገ ውይይት እንጂ ምንም አይነት የድርድር ሥራ እንዳልተካሄደ በመግለጽ አስተባብለዋል:: የሆነው ሆኖ፣ የዐማራው ሕዝብ የተደቀነበትን ሥርዐታዊ የህልውና አደጋ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ገርስሶ ለመጣል ከፍተኛ
መሥዋዕትነት እየከፈለ በሚዋደቅበት በአሁኑ ወሳኝ ወቅት፣ ማንኛውም ወቅቱን ያልጠበቀና ምስጢራዊ ድርድር ወይም የቅድመ ድርድር እንቅስቃሴ፣ ትግሉን አደናቅፎ የዐማራውን ሕዝብ ለዘለዓለም ባርነት የሚያጋልጥ መሆኑ ሊካድ የማይችል ሐቅ ነው።

ስለሆነም፣ ውይይትንም ሆነ ድርድርን በተመለከተ የማያሻማና ብዥታ የሌለው፣ ጥርት ያለ አቋም በሁሉም የዐማራውን የህልውና ትግል እመራለሁ በሚል ቡድንም ሆነ በሚደግፍ ወገን ዘንድ መያዙ አስፈላጊ ነው።

የአገዛዙ ጦር የሞራል እና የውጊያ አቅሙ ተዳክሞ፣ የፀረ ዐማራው ሥርዐት በውድቀት አፋፍ ላይ እያቃሰተ በሚገኝበት ሰዐት፣ ወንጀለኛው መንግሥት ከዚህ ውድቀቱ ተንሰራርቶ ወደ ተለመደው የዐማራን ዘር ማጥፋት ዘመቻ ለመመለስ ከሚጠቀምባቸው ስልቶች ዋናው መንገድ፣ የተለያዩ የፋኖ አደረጃጀቶችን ከፋፍሎ፣ በድርድር እና በውይይት ስም አዘናግቶ ማኮላሸት እንደሆነ ካለፉት የቅርብ ጊዜ የክህደት ታሪኮቹ መረዳት አዳጋች አይሆንም።

የድርድር ዓለማቀፍ ተሞክሮም ቢሆን የሚያሳየው፣ አገዛዞች አንድ ሆኖ ከቀረበ ተደራዳሪ መካከልም እንኳን በጥቅም፣
በድብቅ ፍላጎት ወይም በሥልጣን ሽሚያ የተለያዩ ፍላጎቶች ያሏቸው ተለይተው፣ ተደራዳሪውን በመከፋፈል የድርድር አቅምን ለማሳጣት እና የእነሱን ፍላጎት ለመጫን፣ በስኬት የሚጠቀሙበት የከፋፍለህ ምታ ስትራቴጂ ዋናው መሣሪያቸው
መሆኑን ነው። የታላላቆቹ መንግሥታት ተቋማት ደግሞ በዚህ የመቶ ዐመታት ልምድ ያካበቱና፣ ሚዛኑ በእጅጉ ወደ እነሱ ያጋደለ ነው። በዚህ መሠረት፣ ገና ከወዲሁ ተነጣጥሎ ለዚህ ጥቃት ተጋላጭ መሆን፣ በፋኖ እና በዐማራው ትግል ላይ የሚያስከትለውን አደጋ መገንዘብ ያስፈልጋል።

የዐማራ ዲያስፖራ ግሎባል ፎረም በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደገለጸው፣ የዐማራውን ህልውና የማረጋጥንም ሆነ፣ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የሥርዐት ለውጥ የማምጣትን ጥያቄ የማይመልስ፤ የፋሺስታዊዉን አገዛዝ ዕድሜ የሚያራዝምና በጥገናዊ ለውጥ
የዘረኛውን ሥርዐት በማስቀጠል ዐማራውን ለከፋ ዕልቂት፣ አገሪቷንም ጨርሶ ለመፍረስ የሚዳርግ ድርድር ወይም ውይይት፣ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም:: በመሆኑም፣ ዘላቂ ውጤት ሊገኝ የሚችለው፣ መሰረታዊ ቅድመ ሁኔታዎች ተሟልተው፣ በተለይም የዐማራ ህልውና ትግል መሪዎች የሆኑትን የፋኖ አደረጃጀቶች አንድነት ተከትሎ፣ በግልፅ መርህና የኃይል የበላይነት ላይ ተመርኩዞ ሲከናወን ብቻ ነው። ከዚህ ውጭ፣ በይበልጥም የፋኖን አንድነትና ጥንካሬ አደጋ ላይ
ሊጥል በሚችልና፣ ከስር-ነቀል ሥርዐታዊ ለውጥ ማምጣት ዉጪ፤ የጥቂቶችን የስልጣን ፍላጎት ለማርካት፣ ወይም በውጭ ኃይሎች ግፊት ጊዜያዊ እፎይታን ለማምጣት የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ በጥብቅ ሊወገዝ ይገባል:: ከዚህም አኳያ፣
ፎረሙ ከዚህ በታች የተገለፀውን አቋም ለፋኖ መሪዎችም ሆነ ለመላው የዐማራ ሕዝብና የትግሉ ደጋፊዎች ሁሉ ይገልጻል::

1. የዐማራ ሕዝብ ባለፉት ብዙ አስርት ዓመታት በተለያዩ መንግሥታት ያጋጠመው የህልውና አደጋ የሚወገደው፣ በሥርዐት ለውጥ እንጂ፣ በክልልም ሆነ በብሔራዊ ደረጃ በሚደረግ የስልጣን ክፍፍል ሂደት፣ ወይም በአጠቃላይ በአገሪቱ የጥገና ለውጥ በማድረግ አይሆንም:: በስልጣን ላይ የሚገኘው የኦሮሞ ብልፅግና ፓርቲ መንግሥት፣ የዐማራን ሕዝብ በግልፅ ለማጥፋት ወስኖ በመነሳት፣ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተደገፈ፣ አረመኔአዊ ጦርነት ከፍቶ፣ በአገሪቱ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መጠን በዐማራ ሕዝብ ላይ የዓለም አቀፍ ሕግጋትን የጣሰ ወንጀል እየፈፀመ ይታያል::

2. ⁠በአንጻሩ የዐማራ ሕዝብ እያካሄደ በሚገኘው ራስን የመከላከል ጦርነት አገዛዙን ድል እየመታ፣ ኃይሉን እያጠናከረ በመገስገስ ላይ ይገኛል:: በዚህ ሁኔታ፣ አገዛዙ ወደ ድርድር ለመግባት ፈቃደኛ መስሎ ቢቀርብም፣ ዋናው ዓላማው ፋኖን በመከፋፈል፣ እንቅስቃሴውን ማዳከምና በትናንሽ መደለያዎች ማኮላሸት እንጂ፣ የችግሩ ሁሉ ምንጭ የሆነውን የጎሳ-ጥላቻ ሥርዐት በውዴታ ከሥር መሰረቱ ቀይሮና ስልጣኑን አስረክቦ፣ የዐማራውን መብትና ክብር ተቀብሎ እኩልነትን፣ ዲሞክራሲንና ፍትህን በአገሪቱ ለማስፈን አይደለም::

3. ⁠ምንም⁠ እንኳን ግጭቶችን በሰላምና በድርድር ለመፍታት መጣር ተመራጭና ተጨማሪ የሕይወት መስዋዕትነትና
ውድመት እንዳይኖር የሚረዳ ቢሆንም፣ በስልጣን ላይ ያለው ወንጀለኛ መንግሥት እስካሁን በተግባር ያረጋገጠው ምግባር፣ ሸፍጥ እና ተንኮልን የተጎናፀፈና፣ በባህርዩም ለችግሩ መሠረታዊ መፍትሄ ለማግኘት የፈቃደኝነት ዝንባሌ በፍፁም የማይታይበት ነው። ስለዚህ፣ የግጭቱን መሠረታዊ ምክንያቶች የማያስወግድ፤ በመንግሥት መዋቅር ተደግፎ በዐማራው ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃትና፣ ባለፉት ስድስት ዐመታት ለተፈፀመው የሰብአዊ መብት
ጥስት ወንጀል ሙሉ ተጠያቂነትን የማያረጋግጥ እና፤ በአንድነት የተሰለፉ የፋኖ ኃይሎች በትጥቅ ትግል በተገኘ
የበላይነት ላይ ተመርኩዘው የማይመሩት፣ ማንኛውም የሰላምና የድርድር ተግባር ስኬታማ ሊሆን አይችልም:: ይልቁንም በተቃራኒው የዐማራን የህልውና ትግል አጨናግፎ፣ ሕዝቡንም ለባሰ ሰቆቃና ስቃይ የሚያጋልጥ ይሆናል::

4. በዚህም⁠ መሠረት፣ የዐማራውን ሕዝብ የህልውና ትግል የሚያደናቅፍ፣ ወይም ዘረኛውን ፀረ -ዐማራ ሥርዓት ለማቆየት የሚደረግ፣ ማንኛውንም በሽግግር ወይም በለውጥ ስም የሚካሄድ ውይይትን ወይም ድርድርን፣ የዐማራ ዲያስፖራ ግሎባል ፎረም አጥብቆ ይቃወማል:: የዐማራው የህልውና ትግል መሠረታዊ ምክንያቶች በሥር-ነቀል ለውጥ ተፈትተው፣ ወንጀለኞች ለፍትህ እንዲቀርቡ መደረግ፣ የፋኖ ኃይሎች እና የዐማራ ሕዝብ ወደ ኋላ ሊሉ የማይችሉበት አቋም እንደሆነም ያምናል::

5. የዓለም አቀፍ ማህበረሰቡም ከከፋፋይ አድራጎቶች ተቆጥቦ፣ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማግኘት ጥረት እንዲያደርግ በተደጋጋሚ ማሳሰብ ግዴታ ነው፡፡ በቅርብ ጊዜ እንደተደረገው የፕሪቶሪያ ዓይነት የችኮላ፣ የማግለልና የቆረጣ ስምምነት፣ ከዘላቂ መፍትሄ ይልቅ ችግሩን አባብሶ፣ የሕዝቡን መከራ ከማራዘም በስተቀር ፋይዳ ያለው ውጤት እንደማያስገኝ መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡

Ethio 251 Media

11 Feb, 14:03


⁠6. ይህንኑ⁠ በመረዳት፣ ድርድርም ባይሆን፣ በቅርቡ ከዓለም አቀፍ ማኅበረሰቡ ተወካዮች ጋር ተነጋግረናል በሚል ያሳወቁት ቡድኖችም ሆኑ ሁሉም የፋኖ ኃይሎች፣ የዐማራውን የህልውና ጥያቄ ለመፍታት፣ ሥርዓታዊ ለውጥ ማረጋገጥን ባላቀፈ እና አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን ባላሟላ፣ አካታችም ባልሆነ፣ በማንኛውም ዓይነት ይፋዊም ሆነ ምስጢራዊ ውይይት ወይም ድርድር እንደማይሳተፉ የማያወላውል ማረጋገጫ እንዲሰጡ አጥብቀን
እንጠይቃለን::

7. ከዚህም ጋር ተያይዞ፣ ሁሉም የፋኖ ኃይሎች ልዩነቶቻቸውን አቻችለው፣ ከግለሰብ ወይም የቡድን ፍላጎት በላይ የሕዝባቸውን ህልውና በማስቀደም፣ በአስቸኳይ ኅብረት ለመመሥረት የሚያስችል ውይይት እንዲያደርጉ አጥብቀን እንጠይቃለን:: በዚህ ረገድ፣ የዐማራ ዲያስፖራ ግሎባል ፎረም እስካሁን ሲያደርግ የቆዬውን ያላሰለሰ ጥረት እንደሚቀጥልና ወደፊትም የሚጠየቀውን ማንኛውንም ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁነቱን የሚገልጸው በታላቅ ቁርጠኝነት ነው::

8. በዓለም ዙሪያ የሚኖሩት የዐማራው ሕዝብ የህልውና ትግል ደጋፊ ዲያስፖራ አባሎች፣ ብዙ መስዋዕትነት ተከፍሎ የተደረሰበት እድገት ተጨናግፎ፣ የዐማራ ሕዝብ ሰቆቃ እንዳይቀጥል፣ ማንኛውንም ከፋፋይ እርምጃ አንዲቃወሙ፤ ከመሳተፍም እንዲቆጠቡ፤ አጥብቀን እናሳስባለን። ይልቁንም፣ በአንድ ጃንጥላ ሥር ተሰባስበው፣ የፋኖ አደረጃጀቶችም በህበረት ተናብበው ትግሉን እንዲያራምዱ፣ የሚያስፈልግውን የገንዘብ፣ የቁሳቁስ፣ የዲፕሎማሲ እና የገንቢ ሃሳብ ድጋፍ በማድረግ፣ ታሪካዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ እንጠይቃለን።

የዐማራ የህልውና ትግል ያሸንፋል!
ድል ለፋኖ!

Ethio 251 Media

10 Feb, 16:42


ከየካቲት 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት በዘጠኝ የአውደ ውጊያ ሜዳዎች ሲገረፍ የሰነበተው የአገዛዙ ቡድን የአምስት ንፁሀን ግለሰቦችን ቤት አቃጥሎ ፈረጠጠ።

ከምንጃር ሸንኮራ ወረዳ መዲና አረርቲ ከተማ በመነሳት ወደበረኸት ወረዳ መዲና መጥተህ ብላ ከተማ ወታደራዊ ሬሽን ለማቀበልና የፖለቲካ አመራሮችን ለማሸሽ ለሶስት ቀናት በየጫካው ድረሱልኝ ሲል የሰነበተው የአገዛዙ ወንበዴ ቡድን በከሰም ክፍለጦር አናብስቶች በዘጠኝ የተለያዩ ስትራቴጂካዊ ቦታዎች ላይ ተቀጥቅጦ አስከሬኑን አዝረክርኮ ቁስለኛውን ተሸክሞ እንደ ፖል መንገድ ላይ ተገትሯል።

ከየካቲት 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሶስት ቀናት ያህል በቆስጤ፣ አክርሚት፣ ምንታምር፣ ራዩ፣ ሜጢ፣ ተሬ፣ ወርቁ አገር፣ ጉራምባ እና አጉራቻ በተባሉ ቦታዎች ጠላትን ሲወቅጡት የሰነበቱት የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለጦር ነበልባል፣ተስፋገብረስላሴ ፣ሀይለማርያም ማሞ ብርጌድ በከፊል ባደረጉት የተቀናጀና ኩታገጠም አስደማሚ ኦፕሬሽን ፀረ አማራው የአገዛዙ ቡድን ከፍተኛ ቁሳዊና ሰባዊ ኪሳራን አስተናግዷል።

ይህን ዜና እስካጠናቀርንበት ሰዓት ድረስ ውጊያው እንደቀጠላ መሆኑን የገለፁት የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለጦር ዋና ቃል አቀባይ ፋኖ ወርቁ ደርቤ የጠላት ሀይል በምድር ላይ አለኝ ያለውን ከባድ መሳሪያና የሰማይ ድሮን ተጠቅሞ መንገዱን ለማስከፈት ቢሞክርም አይበገሬዎቹ የከሰም ልጆች ከሚያውቁት መልክዓምድራዊ አቀማመጥ ጋር በመዋሀድ ጠላትን ሙትና ቁስለኛ እያደረጉት ሲገኙ የአማራን ማህበረሰብ ሀብትና ንብረት ማውደም ልዩ መገለጫው የሆነው የአብይ አህመድ ወንበዴ ቡድን የአምስት ንፁሀን ግለሰቦችን ቤት አቃጥሎ አራት የቁም እንስሳትን ገድሎ ድረሱልኝ እያለ ይገኛል ብለዋል።

ድል ለአማራ ፋኖ
ክብር ለተሰዉት
የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል

Ethio 251 Media

08 Feb, 15:58


ሰበር /አሳዛኝ ዜና

በሸዋ ኤፍራታናግድም ወረዳ አገዛዙ በፈፀመው የድሮን ጥቃት የንፁኃኖች ሕይወት አልፏል!

በሁሉም መስክ ኪሳራ አሰያስተናገደ ያለው አሸባሪው የብልፅግና አገዛዝ በተለያየ ወቅት የሚፈፅማቸው ንፁኃንን ዒላማ ያደረጉ የድሮን ጥቃቶች በርካታ ሲቪሊያን ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።

በዛሬው ዕለት ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ገደማ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የፋኖ አባላትና አመራሮች ይኖሩበታል በሚል የተሳሳተ ግምት በኤፍራታና ግድም ዘንቦ ቀበሌ በሰነዘረው የድሮን ጥቃት የግለሰብ መኖሪያ ቤት ላይ ባደረሰው ጉዳት የንፁኃኖች ህይወት አልፏል።

አገዛዙ በግለሰብ መኖሪያ ቤቶች ላይ በፈፀመው የድሮን ጥቃት እናት ከእነ ልጇ ጨምሮ 4 ሲቪሊያን ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ጋር ከ20 በላይ የቀንድና የጋማ ከብቶች ላይ ጉዳትና ውድመት አድርሷል።

የአብይ አህመድ አማራ ጠል አገዛዝ በጋራ ታግለን ልናስወግደው የሚገባ ከባዕድ ወራሪ ያልተለየ አረመኔና ጨካኝ አገዛዝ በመሆኑ በተባበረ ክንድ ሁሉም አማራ በተሰለፈበት መስክ ስርዓቱን ለመቅበር የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ እናቀርባለን።

ክብር ለሰማዕታት
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ
የካቲት 1/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

08 Feb, 15:57


ከአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር የተሰጠ የሀዘን መግለጫ

፨ ሀምሳ አለቃ ፋኖ ሀይማኖት አፍወርቅ በቅፅል ስሙ ካይሮ በመባል የሚታወቀው ጀግናችን ለጠላት እጄን አልሰጥም በማለት ከጠላት ጋር ተናንቆ ተሰውቷል!!

የካቲት 01/2017 ዓም

፨ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ በእነማይ ወረዳ ቢቸና ከተማ ጥቅምት10/1974/ዓም ደሮተራ ሰፈር ተወለደ።ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ እድሜው ለትምህርት ሲደረስ በቢቸና ከተማ ሀይሎ ሴዴቅ የመጀመረያ ደረጃ ትምህርቱን በመከታተል ላይ እያለ ወደ ሀገር መከላከያ ሰራዊት አባል ሆኖ ትምህርቱን አጠናቀቀ።ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ በመከላከያ ሰራዊት ከ15 አመት በላይ ለእናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ከአገለገለ በኅላ በቢቸና ከተማ እነማይ ኮሌጅ accounting diploma ተመረቆ በግል ባንክ በጥበቃ ስራ አገልግሏል።ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ በግል ንግድ የግል ባጃጅ እና አባዱላ በመግዛት ቤተሰቡን እየመራ ነበረ።

፨ ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ ህዳር 24/2014 ዓም በእነማይ ወርዳ የተመሰረተው የአማራ ህዝባዊ ሀይል ፋኖ መስራች ነበር።በእነማይ ወረዳ ቢቸና ከተማ ተወልዶ ያደገው ወንድማችን ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወረቅ በአማራ ፋኖ የትጥቅ ትግል አሻራቸውን ካሳርፉ ጥቂት አመራሮች ውስጥ አንዱ ነበር።

፨ ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ በአርበኛው ዘመነ ካሴ በሚመራው የአማራ ህዝባዊ ሀይል ፋኖ የትጥቅ ትግል በመሰለፍ የንግድ ባንክ ስራውን በመተው በቢቸና ከተማ ከ166(አንድ መቶ ስልሳ ስድስት) የአንደኛ ዙር የፋኖ አባላትን አሰልጥኖ አስመረቋል።ከተመረቁት ሰልጣኞች ውስጥ 43 (አርባ ሶስት) ምልምል የፋኖ አባላትን በመያዝ ከቢቸና ከተማ የትግል ጓዶቹ ጋር በመሆን ከአማራ ህዝብ ሂሳብ አወራርዳለሁ ካለው የTPLF ሰራዊትን ለመፋለም በሰሜኑ ጦርነት ከቢቸና ከተማ በመነሳት እስከ ደቡብ ወሎ ሀይቅ ከተማ ድርስ በመሄድ የአማራን ህዝብ የህልውና ትግል ተሳትፏል።

፨ ጀግናው ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ ከሰሜኑ ጦርነት በኅላ በምስራቅ ጎጃም ዞን ባሉ ወረዳወች በመዘዋወር የአማራ ህዝባዊ ሀይል ፋኖ አደረጃጀት በማገዝ አሻርውን አሳርፏል።ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ በቀድሞው የአማራ ህዝባዊ ሀይል ፋኖ በእነማይ ወርዳ በላይ ብርጌድ በአሁኑ አባ ኮስትር ብርጌድ ውስጥ ጦር አዛዥ፣የአባ ኮስትር ስልጠና መምሪያ፣የአባ ኮስትር ብርጌድ 1ኛ ጠቅል ሻለቃ ጦር አዛዝ በመሆን በወረደው ውስጥ በተደርጉ አውደ ውጊያወች በሙሉ ተሳትፏል።

፨ ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ በአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አባ ኮስትር ብርጌድ ልዩ ኮማንዶ ለ6 (ስድስት) ወራት በልዩ ብቃት አሰልጥኖ አስመረቋል።ፋኖ ሀይማኖት አፍወርቅ በአባ ኮስትር ብርጌድ ስልጠና መምሪያ በተሰጠው የስራ ዘረፍ ሀላፊነቱን በብቃት በመወጣቱ የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ስልጠና መምሪያ ሀላፊ በመሆን እየሰራ ባለበት ሰዓት ጥር 30/2017 ዓም በክፍለ ጦሩ በተሰጠው የስራ ግዳጅ በእነማይ ወረዳ የረዝ ቀበሌ ላይ ከጥዋቱ 3:00 ሰዓት በተደረገበት ከበባ እና እልህ አስጨረሽ ውጊያ በኅላ እጄን ለጠላት አልሰጥም በማለት ከጠላት ጋር ተናንቆ ለተከበርው የአማራ ህዝብ ውድ ህይወቱን ሰጥቶ አልፏል።ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ ጥር 30/2017 ዓም በእነማይ ወረዳ ዲማ ቅዱስ ጊዮወርጊስ በክብር የትግል ጎዶቹ በተገኙበት ስረዓተ ቀብሩ ተፈፅሟል።

ለአማራ ህዝብ የህልውና ትግል በጀግንነት የተሰዋህው ጓዳችን/ወንድማችን ፋኖ ሀምሳ አለቃ ሀይማኖት አፍወርቅ ነፍስህን ከደጋጎች ጋር ያኑረልን 😭😭😭

ከአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር የምንገኝ የትግል ጎዶችህ
''የጀግና ሞቱ እረፍቱ''
ጀግና ይሰዋል!
ትግል ይቀጥላል!

Ethio 251 Media

08 Feb, 15:55


ሰበር ዜና!

በዛሬው እለት በቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ የቀስተ ደመናና የጅበላ ሙተራ ብርጌዶች ቸርተከል ንዑስ ከተማ ላይ በሰሩት የተቀናጀ ኦፐሬሽን ጥሩ ድል አስመዝግበዋል።

ይህ ጠላት አሳሽ ሃይል ተብሎ በየቦታው ይንቀሳቀስ የነበረ ኃይል ሲሆን ዛሬ በተደረገበት መብረቃዊ ጥቃት በርካታ ኪሳራ ደርሶበታል።

በዚህ ውጊያ ሶስት መሳርያና በርካታ ተተኳሽ በፋኖ የተማረከ ሲሆን እስካሁን በደረሰን መረጃ አራት ፓትሮልና አንድ ኦራል የጠላት ሙትና ቁስለኛ መነሳቱን የአይን እማኞች አረጋግጠውልናል።

ጠላት በአሁኑ ሰዓት እንዳጠቃለይ እንደ አማራ በሚያደርገው ወረራ በአመዛኙ በጎጃም ውስጥ ትልቅ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ሲሆን በተለይ በዚህ ቀጠና ከፍተኛ ክምችት ያለው የመሳርያና የሰው ኃይል እያንቀሳቀሰ ይገኛል።ይሁን አናብስቱ የስድስተኛ ክፍለ ጦር ፋኖዎች በሚሰሩት እረፍት የለሽ ውጊያ ጠላት አሁንም ክፉኛ እየተጎዳ ይገኛል።

ድል ለአማራ ፋኖ!
ክብር ለሰማዕቶቻችን
አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተስፋ፣አዲስ አስተሳሰብ

ፋኖ ኢንጅነር ዘመን ባሳዝነው

Ethio 251 Media

08 Feb, 13:51


ሰበር ዜና

አማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አምሓራ) ምዕራብ ወሎ ኮር ዳግም ክተት ወረኢሉ ክፍለጦር 7ለ52 ብርጌድ ንስር ሻለቃ ለገሂዳ ወረዳ ላይ ታላቅ ድል ተጎናፀፈ።

ጀግኖቹ በለገሂዳ ወረዳ የሚገኘውን የአገዛዙን ዙፋን አስጠባቂ ሀይል ካምፕ አድርጎ በተቀመጠበት የለገሂዳ ወረዳ ምክርቤት ግቢና ደፈጣ ብለው በወጡበት አድሱ ጤና ጣቢያ ወይም ማጀቴ በመባል በሚጠራው ቦታ ላይ ዶግ አመድ በማድርግ ጥላትን አንገት አስደፍቶ አዋርዶና አሸማቆ በመውጣት ታላቅ ድል ሰርተዋል።

በተጋድሎው ብዛት ያለው ጠላት የተደመሰሰ ሲሆን ከአምስት በላይ ቁስለኛን አስተናግዶ በአጠቃላይ ሙትና ቁስለኛዉን ታቅፎ በስነ ልቦናም ተሸማቆ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው ሲል የ7ለ52 ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት ፋኖ ሙሃመድ ሽፈራው ገልጿል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ- አምሓራ)
የካቲት 1/2017 ዓ.ም

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Feb, 19:32


አገዛዙ ህዝብን መዝረፉን አጠናክሮ ቀጥሎበታል!

የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ከጦርነቱና ዘር ማጥፋቱ ባሻገር የህዝብን ንብረት መዝረፉንና ወደ ድህነት ብሎም ብልፅግና መር ረሃብ ለመፍጠር የሚያደርገዉን ጥቃት አጠናክሮ ቀጥሎበታል::

የአገዛዙ ሰራዊት ሰሜን ምስራቅ ዕዝ ራያ ቆቦ ልዩ ስሙ ጎለሻ የሚባል ቀበሌ ላይ ከ80 ኩንታል በላይ ማሽላ ህዝቡን በመደብደብ አስገድዶ ዘርፏል:: ለፋኖ ስንቅ ትሰፍራላችሁ በሚል ሰበብ ህዝቡን በጅምላ በመደብደብ ቤት ለቤት እየገባ ከሰማኒያ ኩንታል በላይ ማሽላ በመዝረፍ በኦራል ጭኖ ወደ ቆቦ ከተማ ወስዷል::

ሰራዊቱ በቅርቡ ከዞብል እስከ ዋጃ ባለው ቀጠና በነበረው ከባድ ዉጊያ በአሳምነው እና ሐውጃኖ ክፍለጦሮች ከፍተኛ ኪሳራ ስለደረሰበት ከፋኖ ጋር ሆናችሁ መረጃ ከመስጠት ጀምሮ ደጀን ሆኖ እስከ መዋጋት ደርሳችሗል በሚል ምክንያት ቤት ለቤት እየገባ ዘረፋ ፈፅሟል::

Ethio 251 Media

07 Feb, 17:29


https://twitter.com/i/broadcasts/1YqKDZPRMeDJV

Ethio 251 Media

07 Feb, 16:23


የሦስት ሚዲያ ጋዜጠኞች ምን አገናኛቸው | አዲሱ ስብስብ የያዛቸው ልዩ ጉዳዮች

አጋፋሪ ፖድካስት

https://youtu.be/mAc0F8kC7xQ?feature=shared

Ethio 251 Media

07 Feb, 14:10


ሰበር ዜና!

ነበልባሎቹ በዕለተ ዮሐንስ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ በሰነዘሩት ጥቃት ጀብድ ሰሩ።

የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለ ጦር የነበልባል ብርጌድ ስር የሚንቀሳቀሰው ሺ አለቃ አራት ቀጫጭኖቹ ፋኖች ከባልጪ ከተማ በመንቀሳቀስ ዛሬ በጥር 30/5/2017ዓ.ም በምንጃር ሸንኮራ በታላቅ ድምቀት የሚከበረውን በፈዋሽነቱ የሚታወቀውን የሸንኮራ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን በዓል ለማስከበር እና ፖለቲካዊ ፍጆታ ለማግኘት ወደ በሳ እና ዮሐንስ ያመራው የአገዛዙ ወንበዴ ሀይል ታቦታቱ በክብር ወጥቶ ከገባ በኋላ በ 8:00 ፋኖ ወዳለበት በቆረጣ የተንቀሳቀሰውን አሰስ ገሰስ አረመኔ ሰራዊት በሃምሳ አለቃ ፍቃዱ የሚመራው ነበልባል ብርጌድ ተፈንጣሪ ሺ አለቃ ሦስት ፋኖች ባደረጉት ደፈጣ የአገዛዙን ደንገጡር ሰራዊት እንዳይሆን አድርገው 4 ቁስለኛ 3 ሙት አድርገው ወደመጣበት የመለሱት ሲሆን አገዛዙ እሬሳውን ለክብረ በዓሉ የመጡ አንጋሾችን ነጠላ በመንቀጥ እየለበሱ እሬሳና ቁስለኛ ያነሱ መሆኑን ከአይን እማኞች አረጋግጠናል።

ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ነፃነታችንን በክንዳችን!!!
አዲስ ተስፋ።
አዲስ ትውልድ።

መረጃው/የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለ ጦር ነበልባል ብርጌድ ፋኖ ነው። 

     ጥር 30/5/2017ዓ.ም
         ነበልባሎቹ።

Ethio 251 Media

07 Feb, 13:04


የአገዛዙ ግፍ!

በትናንትናው ዕለት በኮሎኔል ድባቤ የሚመራው የብርሃኑ ጁላ ጦር ከሰከላ ግሽ አባይ ከተማ ተንቀሳቅሶ የነበረ መሆኑን እና ከጥዋቱ 2:00-9:00 አሸባሪውን ሀይል ግዮን ብርጌድ በከበባ ሲቀጠቅጡት መዋሉን መዘገባችን የሚታወስ ነው። ከ9:00 በኋላ ግዮን ብርጌድ መንገዱን ከፍተው ጠላትን ወደ እሮቢት አሳልፈውታል።

ጠላት እግሬ አውጭኝ ብሎ እየፈረጠጠ እያለ አይበገሬዎቹ ዘንገና ብርጌድ ጠላትን እሮቢት ላይ ደፈጣ በመያዝ በብሬል እና በስናይፐር አቀባበል አድርገውለታል። በዚህም አናብስቶቹ የደፈጣ መሀንዲሶች ዘንገና ብርጌድ ሁለት ጥቁር ክላሽ ማርከዋል። በዚህ ሀፍረትን የተከናነበው ኮሎኔል ድባቤ ከባድ መሳሪያ ሞርተር 120 በመተኮስ ዋጋዬ ጎበዜ የተባለች የ65 አመት እናት ዜና አዲስ የ9ኝ አመት ፣ ፍቅር አዲስ የ17 አመት 2 የልጅ ልጆቿ እና ከ7 ቁም ከብቶች ጋር በግፍ ተጨፍጭፈዋል።

በትናንትናው ዕለት ግዮን ብርጌድ መብረቁ ሻለቃ 7 ጥቁር ክላሽ እና ከሦስት ሽህ በላይ በዛት ያለው ተተኳሽ መማረክ የቻለች ሲሆን አይበገሬዎቹ ሃይሌ አድማሱ ሻለቃ 2 የአገዛዙ ወታደር ከነ ጥቁር ክላሻቸው መማረክ ችለዋል።

ግትም ሽለቃ በ10 አለቃ የቆዬ፣ የሃይሌ አድማሱ ሻለቃ በጀግኖቹ መሉጌታ አዱኛው ሻለቃ መሪነት ፣ በፈኖ ሮቤል እና ፋኖ ወርቁ ይታይህ ዘመቻ መሪነት የተመራ ሲሆን መብረቁ ሻለቃ በጀግናው ፋኖ እንደሻው ጌታነህ እና በነፍጠኛው ሻለቃ አበጀ እየተመራ ጠላትን በመናበብ እንደ እባብ ሲቀጠቅጡት ውለዋል።

በሌላ በኩል የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ኛ ክፍለጦር ግዮን ብርጌድ በክንደ ነበልባሉ ሻለቃ ደምስ የሚመራው አባግስ ሻለቃ ወደ ሰከላ ግሽ አባይ ከተማ ዘልቀው በመግባት 4 የአገዛዙ ወታደር የደመሰሱ ሲሆን አድማ ብተናን እና ባንዳ ሚኒሻን ሲያሳድዱት ውለዋል።

በዚህ አውደ ውጊያ 15 የአገዛዙ ወታደር የተደመሰሰ ሲሆን ብዛት ያለው የአገዛዙ ወታደርም ሊቆስል ችሏል።

በአጠቃላይ በትናንትናው ዕለት ከ2:00-11:00 አውደ ውጊያ የተካሄደ ሲሆን ያለምንም መስዋዕትነት አናብስቶቹ ግዮን ብርጌድ ጠላትን ሲቀጠቅጡት ውለዋል። በዚህ አውደ ውጊያ የፋኖን የበላይነት ያረጋገጠ እና የአገዛዙን ሰራዊት ተስፋ ያስቆረጠ ሆኖ ተመዝግቧል።

የተማረኩ ቁስለኞችንም ፋኖ እያሳከመ ይገኛል። አሸባሪው አብይ አህመድ እንደሚለው ፋኖ ዘራፊ እና አሸባሪ ሳይሆን የአለም አቀፍ ህጎችን የሚያከብር የነጻነት ታጋይ ነው።

ሙሉ የምርኮኞችን ቃለ መጠይቅ ለመላው የአማራ እና የኢትዮጵያ ህዝብ በቅርብ ቀን እናደርሳለን።

ፋኖ የቻለ አድማሱ
የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ኛ ክፍለጦር የግዮን ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት

Ethio 251 Media

07 Feb, 11:38


አማራነትን ማዳን ፣ አማራነትን ማስቀጠል ይፈልጋሉ? መልስዎ አዎ ከሆነ
Dallas:- February 16
Los Angeles:- February 23
Chicago:- March 1
Toronto:- March 15
Seattle:- March 15
Las Vegas:- March 26
Washington DC:- April 5
ዝግጅቶች ላይ በመገኘት ድጋፍዎትን ያድርጉ!!!

Ethio 251 Media

06 Feb, 17:48


የዛሬ ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-

https://twitter.com/i/broadcasts/1YqGooewXYgGv

https://rumble.com/v6hpbk7--251-251-zare-february-6-2025-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

06 Feb, 15:22


ሰበር ዜና

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) የምስራቅ አማራ ኮር 1 በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የሚመራው ባለሽርጡ ክፍለጦር በሰሜን ወሎ ሀብሩ ወረዳ ልዩ ቦታው ፋጂና መነዮ በተባለ ስፋራ ታላቅ ድል ተጎናፀፈ፡፡

በተደረገው ተጋድሎ የስርአቱ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት የባለሺርጡ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃን ለማፈንና ለመክበብ የተንቀሳቀሰው የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ የዙፋን ጠባቂውን ከበባ በትንሽ መስዋዕትነት በመስበር በርካታ ጠላት ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ሰርተዋል::

በዚህም የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት ከለሊቱ 11:30 ከጊራና ወደ ፋጂ ሲንቀሳቀስ መረጃ እንዳይወጣበት በመስኖ አትክልት ሊያጠጡ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ንፁሀን ገበሬዎችን እንዳይንቀሳቀሱ ካገተ ቡሀላ የሻለቃዋን በትር መቋቋም ሲያቅተው ወደ ኀላ ሲመለስ ተስፋ በመቁረጥ 10 ንፁሀን ገበሬዎችን በአሰቃቂ ሁኔታ ጨፍጭፏል፡:

በቀጣይም መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
ጥር 29/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

06 Feb, 14:36


እነዚህ የአማራ ህዝብ እሴቶችአማራነታችንን የገነቡ የስነ ልቦና ውቅሮች ናቸው። አቃቤ ህግ አንዳችም ማስረጃ ማቅረብ አይችልም እንጅ ኢትዮጵያ በእነዚህ የአማራ እሴቶች ብቻ መመራት ይኖርባታል'' የሚል አቋም ብይዝ እንኳን ጉዳዩ የፖለቲካ ሙግትና ውይይት፤ ክርክርና ድርድር አጀንዳ እንዲሁም ለመራጭ ዜጎች ይሁንታ የሚቀርብ የምርጫ ኮረጆ ጉዳይ እንጂ በወንጀለኝነት የሚያስጠይቅ አይደለም። ይህ የአቃቤ ህግ ክስ ግን መንግስት ከአማራና ከአማራነት የፀዳች ኢትዮጵያ ነው ወይ የሚፈልገው የሚል ሙግት ያስነሳል። ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ከአማራና አማራነት በስተቀር እንዲሆኑ የሚደነግግ ህግስ አለወይ?ሶስተኛ፦ በአቃቢ ህግ ክስ ላይ ቋሪትና ደጋ ዳሞት ላሉ የሽብር ቡድን አስተባባሪዎች በስልክ ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም በመደወል መከላከያን ማጥቃት ህገ መንግስታዊ መብት መሆኑን በማሳወቅ እንዲመቱት ትዕዛዝ ሰጥቷል የሚል ነው። አቃቤ ህግ ለዚህ ክሴ አስረጅ የሚሆን አንዳችም ማስረጃ አላቀረበም። የተደወለበትና የጥሪ ተቀባይ ስልክ ቁጥሮች እንዲሁም የትዕዛዝ ተቀባይ ግለሰቦች ማንነት አልቀረበም። በቀረበ የማስረጃ ዝርዝር ላይም በተሰጠው ትዕዛዝ መነሻነት በቋሪትና ደጋዳሞት ወረዳዎች የተጎዱ ሰዎችና ንብረት ዝርዝርም አልቀረበም። የፍሬ ነገር ክርክር ሲደረግ የማቀርበው እንደተጠበቀ ሆኖ የወቅቱ የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር የነበሩት ዶ/ር ይልቃል ከፋለ የፌደራል መንግስት የፀጥታ ኃይሉን ወደ ክልሉ እንዲገባ የጠየቁት ሐምሌ 27/2015 ዓ.ም ነው። የመከላከያ ሰራዊት ወደ ደጋ ዳሞትና ቋሪት መግባት የሚችለውም ርዕሰ መስተዳደሩ ጥያቄ ካቀረቡ በኋላ በመሆኑ ሐምሌ 25/2015 ዓ.ም አቃቤ ህግ በክሱ ርምጃ ይወሰድበት ብለሃል ያለውን መከላከያ በምን አግባብ ቋሪትና ደጋዳሞት ሊገባ ቻለ የሚል ከባድ የህገ መንግስታዊነት ጥያቄ የሚያስነሳ ነው።

የተከበረው ችሎት፤ ክቡራን ዳኞች፤

አቃቤ ህግ በስልክ ትዕዛዝ ሰጥቷል በሚል የሁለት ግለሰቦች ንግግር የያዘ ድምፅ አዳምጨዋለሁ። አቃቤ ህግ በስሜ በተመዘገበ የታወቀ ስልክ ቁጥር ስለመደወሌ፣ የደወልኩበትን ስልክ ቁጥር እና አስተባባሪ ነው ያለውን ግለሰብ ስም አላቀረበም። ለመሆኑ በማስረጃነት ያቀረበው የድምፅ ቅጅ የኔ ስለመሆኑ በምን አረጋገጠ? በምን መሳሪያ መረመረው? ኢትዮጵያ የድምፅ አሻራ መመርመሪያ መሳሪያና በዚህ መስክ የሰለጠነ ባለሙያ የላትም። የት አስመርምሮት? ምን ያህል ፐርሰንት ከእኔ የትኛው ኦሪጅናል ድምፅ ተነፃፅሮ ምስስሎሽ ተገኘበት? እንደ አገርስ የድምፅ ምስስስሎሽ መቁረጫው መቶኛው(cut -off percentage) ምን ያህል ሲሆን ነው ህጋዊ ውጤት የሚኖረው?
እነዚህ ቁልፍ ጉዳዮች እንደተጠበቁ ሆነው እና የቀረበው የድምፅ ማሰረጃ የእኔ አይደለም እንጅ፤ ቢሆን እንኳን ወንጀል የሚያቋቁም አንዳችም የህግ ጥሰት ግን አላገኘሁበትም።

በመጨረሻም፦ አቃቤ ህግ ያቀረበው የፀና ፈቃድ ሳይኖር የጦር መሳሪያ መያዝ ጉዳይ ህጋዊ ፈቃድ ያለኝ፣ የፈቃድ ደብተሩንም ለ8 ወራት ይዘውት ቆይተው የመለሱልኝና ማቅረብ የምችል መሆኔን ለችሎቱ አስታውቃለሁ።

አመሰግናለሁ
አቶ ክርስቲያን ታደለ ፀጋዬ

Ethio 251 Media

06 Feb, 14:35


በአቃቢ ህግ በክስነት የቀረቡ አንዳንድ ጉዳዮች ላይ ለተከበረው ችሎት ማብራሪያ መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘሁት ክቡራን ዳኞች እንዳቀርብ ትፈቅዱልኝ ዘንድ በአክብሮት እጠይቃለሁ።

አንደኛ፦ እኔ ክርስቲያን ታደለ ፀጋዬ ዛሬ በዚህ ችሎት በተከሳሽነት የቆምኩት፤ ለ550 ቀናትም በግፍና ችካኔ እገታ ውስጥ የምገኘው ለአንዲት ደቂቃ እንኳን በጥፋተኝነት የሚያስቀጣ አንዳችም የወንጀል ድርጊትን የሚያቋቁም የህግ መተላለፍ ስለፈፀምኩ አይደለም። ይልቁንም የአማራ ህዝብ የሚያነሳቸውን የህልውና ጥያቄዎች በይፋ በማቅረቤ፤ በህዝቤ ላይ የሚደርሰውን ግፍና በደል በማስረጃ በመመሞገቴ፣ የገዠውን ፓርቲ አፈናና የመንግስት አሰራሮችንና አመራሮችን ብልሹነትና ዘረፋ በመታገሌና በማጋለጤ ነው። ያደረግኋቸው ትግሎችና ማጋለጦች በሙሉ በህጋዊ መድረኮችና አማራጮች ያደረግኋቸው ናቸው። ራሴው ጭምር በኮሚቴ አባልነት ተሳትፌባቸው የተረጋገጡ አማራውን በጅምላ የመግደል፣ማፈናቀልና ማሳደድ ዘር ተኮር ጥቃት ሪፖርቶች፣ የኢትዮጵያ ሰባዊ መብት ኮሚሽን በተለያዩ ጊዚያት ያወጣቸውን ሪፖርቶች እንዲሁም ልዩ ልዩ አገር በቀልና ዓለም አቀፍ የሰባዊ መብት ተቋማት ያወጧቸውን ሪፖርቶች በመያዝ መንግስትና ገዘው ፓርቲ ብልሹ አሰራሮችንና አመራሮችን እንዲያስተካክል ታግያለሁ። ይህንንም በቀጥታ የሬድዮና የቴሌቪዠን ስርጭት ባገኘው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ያደረግሁት ነው።

በምክር ቤቱ በመንግስት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢነቴ በነበረኝ ኃላፊነትም በፌደራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የተከናወኑ የኦዲት ሪፓርቶችን መሰረት በማድረግም የከፋ ችግር ያለባቸውን ተቋማት አሰራራቸውን፣ አደረጃጀታቸውን እና አመራራቸውን እንዲያሻሽሉ የመገምገም ስራ ሰርቻለሁ። ተደጋጋሚ የአመራር ብልሹነት ያሳዩ አካላትም የወንጀልና ፍትኃብሔር ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ ክስ እንዲመሰረት ፍትህ ሚኒስቴርን አዝዣላሁ። በምክር ቤት አባልነቴም ጠቅላይ ሚኒስቴሩን ጨምሮ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በአሰራራቸው የፋይናንስ ግልፀኝነትና ህጋዊነትን እንዲከተሉና እንዲያረጋግጡ እንዲሁም ኦዲት ለመደረግ ፈቃደኝነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጠይቂያለሁ።
እነዚህን ጥያቄዎች እንዳልጠይቅ አንዳንድ አመራሮች በግል በኢመደበኛ ሁኔታ ለማግባባት ሞክረዋል። አንዳንዶቹም ሊያስገድሉኝ፣ ሊያሳስሩኝና አንዳች አይነት ጉዳት ሊያደርስቡኝ እንደሚችሉ ጭምር ነገረውኛል፤ መልዕክትም አድርሰውኛል። ይህ ሁሉ የሆነው ያጎደልኩት ስነ- ምግባር አልያም የተላለፍኩት ወንጀል ስለነበር አልነበረም። ይልቁንም ያደረግሁት ሁሉ በህዝብ እንደራሴነቴ ህዝብና ህግ የጣለብኝን ግዴታ እና ኃላፊነት ነው የተወጣሁት። ያደረግሁት ሁሉ የሚያሸልም እንጅ የሚያስነቅፍ አልነበረም። እጅግ ሲከፋም አሁን ባለሁበት ሁኔታ የግፍ ሰለባ የሚያደርገኝ መሆን አልነበረበትም።

የተከበረው ችሎት፤ ክቡራን ዳኞች፤

ቀደም ብዬ እንዳወሳሁት ለ550 ቀናት በአስከፊ ሁኔታ የተሰቃየሁት፤ ለቀጣይ ለማይታወቁ የሰቆቃ ሌሊቶችም በአገታ የምቆየው አንዳችም ወንጀል ስለፈፀምኩ አይደለም። ማን እንዳሰረኝ፣ ለምን እንደሰረኝ አውቃለሁ። እውነታውን ፈጣሪ፣ ህዝቡም ያውቃል።

ሁለተኛ፦ እኔ አማራ የሆንኩት አማራ ሆኘ ስለተወለድኩ ነው። የአማራ ብሔርተኝነት አቀንቃኝ የሆንኩትም ፈቅጀ፣ መርጨና ወድጄ ነው።በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ለአማራነቴ ጥብቅና መቆምም ተፈጥሯዊ ግዴታዬ ነው። በዚህም በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሱ ያሉ ስርዓታዊ፣ ተቋማዊ ህገመንግስታዊ ሁለንተናዊ በደሎችና መገፋቶችን ለማስቆምና የህዝባችንን ዘላቂ መብቶች፣ ፍላጎቶችና ጥቅሞችን ለማስከበር የአማራ ህዝብ የህልውና ጥያቄዎች ናቸው ብሎ በለያቸው የፓለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አጀንዳዎች ላይ ፕሮግራምና ፖሊሲ በመቅረፅ እንዲሁም የመመስረቻ ማንፌስቶ በማዘጋጀት ከትግል ጓዶቼ ጋር በመሆን በምርጫ ቦርድ በህጋዊ መንገድ ተመዝግቦ በህጋዊ መንገድ የሚንቀሳቀስ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ የተሰኜ ፓርቲ አቋቁሚያለሁ። በ6ኛው ዙር አገር አቀፍና ክልላዊ ምርጫም 5 የፓርላማና 13 የክልል ምክር ቤት ወንበሮችን አሸንፈናል። ባነኘነው ወንበርና በመራጮች ድምፅ ብዛትም የኢትዮጵያ ትልቁ ተቃዋሚ ፓርቲ ነው።

እኔም የህዝብ እንደራሴ የሆንሁት ገዠውን ፓርቲ ጨምሮ ከተፎካካሩ ሌሎች 8 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወዳድሬ አሸንፌ ነው። በምርጫ ማንፌስቷችን፣ በመመስረቻ ጽሑፋችን በልዩ ልዩ መድረኮች ባካሄድናቸው የምርጫ ክርክሮች ጭምር የህዝባችንን እሴቶች እንደምንጠብቅ፣ የአማራ ብሔርተኝነት የማደራጃና የርዕዮተ-ዓለም ማዕቀፋችን እንደሆነ እንዲሁም ህዝቡ መርጦን መንግስት ከሆን የህዝባችንን የህልውና ጥያቄዎች እንደምንመልስ ተከራክረናል፣ ቃል ገብተናል። አማራዊ እሴታችን ለእኛ ቅዱስ ነው። እኛነታችን ከደምና ስጋ ብቻ ሳይሆን ከአማራዊ እሴት ጭምር የተሰራ ነው። በዚህም ደስተኞች ነን።

ይሁንና አቃቤ ህግ ባቀረበው የፖለቲካ ውንጀላ ሰነድ ላይ ''አማራ ርስቱን ተቀምቷል፤ አገሪቱ በአማራ እሴት መመራት አለባት'' የሚል የርዕዮተዓላማዊ አቋም መያዛችን ክስ ሆኖ ቀርቧል።

የተከበረው ችሎት፤ ክቡራን ዳኞች፤

''የአማራ ህዝብ የህዝብና ግዛት አንድነትና ኢ-ተነጣጣይነት ተገርስሷል'' የሚለው እውነት እኔ ብቻ ሳልሆን መላው አማራና በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚጋሩት ኃቅ፣ ፓርቲዬ አብንም በመመስረቻ ሰነዱና በምርጫ ማንፌስቶው በግልፅ ያሰፈረው፣ ያሁኑ የአማራ ብልፅግና የቀድሞው አዴፓ በ12 መደበኛ ጉባኤው ተገቢነቱን አምኖ የሚታገልለት የአማራ ጥያቄ መሆኑን በይፋዊ መግለጫ ጭምር የተቀበለው ነው። የፌደራል መንግስቱም የአማራ ህዝብን ጨምሮ በሌሎችም ብሔረሰቦች የሚቀርቡ የማንነትና ወሰን ጉዳዮችን እልባት ለመስጠት ኮሚሽን እስከ ማቋቋም መድረሱ፣ አሁን በስራ ላይ ባለው አገራዊ ምክክር ኮሚሽንም እንዲፈቱ ከተያዙ ቁልፍ አገራዊ አጀንዳዎች አንደኛው መሆኑን ወስዶታል። ታዲያ እንዴት ክስ ሆኖ እኛ ላይ በልዪነት ሊቀርብ ቻለ?
እሴትን በተመለከተ ለችሎቱ ለማስገንዘብ ያህል፦
እሴት ማለት የጋራ የሆነ ማህበረሰባዊ የነገሮች ምልከታ ሆኖ የማህበረሰብ አባላት በግልና በጋራ የሚያከናውኗቸውን የየዕለት ተግባራትና እሳቤዎች ጥሩነት አልያም መጥፎነት እንዲሁም ተገቢነቴና ኢ-ተገቢነት መለያ መርኋቸው ነው።

የአማራ እሴት ማለት የማንነቱ መገለጫዎች የሆኑት ለአብነትም አማኝነት፣ለጋስነት፣ ሩህሩህነት፣ ይቅርባይነት፣ደግነት መልካምነት፣ ኃቀኝነት፣ጀግንነት፣ ሰውዳድነት፣ ሰው አክባሪነት፣ ግልፅነት፣ ትሁትነት፣ እንግዳ ተቀባይነት፣ ቀናዒነት፣ አርበኝነት፣ ህግ አክባሪነት፣ ፍትኃዊነት፣ርቱአዊነት፣ ታማኝነት፣አስተዋይነት፣ ጥበበኝነት፣ ገርነ፣ ትዕግስተኝነት፣መንፈሰ ጠንካራነት ጥቂቶቹ ናቸው።

Ethio 251 Media

06 Feb, 13:12


በአጠቃላይ እኔም ሆንኩኝ በሽብር ወንጀል ስም የታገትን አማራዎች ህግን በመተላለፍና ወንጀል በመፈጸማችን ሳይሆን አማራዎች፣ ፖለቲከኞችና ምሁራን በመሆናችንና የስራቱን ዘረኝነና አልጠግብ ባይነት፣ ገዳይነትና አማራ ጥዕልነት፣ አፋኝነት፣ የተወሰነ ቡድን ጥቅም አስከባሪነትና አገር አጥፊነት ፣ ህግናስርዓት አልበኝነት ህጋዊ በሆነ መልኩ በመታገሳችንና ለህዝብ ድምጽበመሆናችን ነዉ።

በስርዓቱና የስራዓቱ መሳሪያከሆኑት ተቋማት ዉስጥ ከሳሽ የሆነዉ የፍትህ ሚኒስቴር(ጠቅላይ አቃቢ ህግ) በሚያቀርቡት ዉንጀላ ላይ ምንም አይነት እምነት የሌለኝ መሆኑን በዚሁ አጋጣሚ ላቀርብ እወዳለሁ። አንደኛ ተቋሙ የቤተሰብና የግል ተቋም ወደ መሆኑ መቃረቡ በአጭሩ የአብይ አህመድ ጓደኞች ባልና ሚስትየግል ሃብት ወደ መሆኑ በመዉረዱ፣ የዝርፊያና የሙስና መናሃርያ በመሆኑራሱ ከሳሽና የተቋሙ ባለሙያዎች የአማርን ዘር ለማጥፋት ደብዳቢና አሰቃይ ሆነዉ በመገኘታቸዉ የጥላቻና የቂም ክስ እንጂ የህግ መሰረት የሌለዉ መሆኑ ቀደም ብዬ በገለጽኳቸዉ ማስረጃዎች የትረጋገጠ ነዉ።

ስለሆነም የቀረበብኝን ዉንጀላና አሉባልታ አልቀበልም። ወንጀልም አልፈጸምኩም። ፍትህ የለም እንጂ ፍትህ ካለ እኔ ነጻ ሰዉ ነኝ። ፍርድ ቤቱ በነጻ ለቆ ለደረሰብኝ በደል ሁሉካሳ ሊያሰጠኝ በቻለ ነበር። ግን እንዴት ሆኖ/ ራሱ ነጻ ያልሆነ ማንን ነጻ ሊያደርግ ይችላል።

አመሰግናለሁ
አቶ ዮሐንስ ቧያሌው ፋሪስ

Ethio 251 Media

06 Feb, 13:12


የአቶ ዮሐንስ ቧያሌው ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስትና ሽብርወንጀል ችሎት በቀረበ ክስ ላይ የተሰጠ የምነት ክህደት ቃል!

የፍትህ ሚኒስቴር (የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ) በ18/07/2016 ዓ.ም በእኔና በእኔ ስም በሚጠራው መዝገብ ላይ ያቀረበዉ ክስ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነትየለዉም።

ለምን
1ኛ ሁሉም የክስ ጭብጦች በፈጠራ የተሞሉ ናቸዉ። የሽብር ቡድን አመራር በመሆን ፣አባል በመሆን ፣ራሱን በመሰየም፣በማደረጃት ፣ ሰራተኛ ሰነድ በማዘጋጀትና ጽንፈኛ ፋኖን በመምራት የሽብር ወንጀል ፈፅሟል ይላል። የተጠቀሰው ሃሳብ በአንድ በኩል መረጃ አልባና ከእኡነት የራቀ ሲሆን በሌላ መልኩ ደግሞ አንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ለመክሰስ የሞከረ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። መረጃ አልባነቱ ማን የሚባልየሽብር ቡድን እኔ አመራር የሆንኩበትና የአመራር ደረጃዬን የገለጸ ካለመሆኑም በላይ በህግ ወይም በ ኢፌድሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተሰየመ አሸባሪ ቡድን ማን እንደሆነ በዚህ ቡድን ላይ የእኔሃላፊነትና የፈጸምኩት ወንጀል ምን እንደሆነ ከመግለጽ ይልቅ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ራሱ በጭንቅላቱ የፈጠረው አሸባሪና ጽንፈኛ ቡድን አመራርና አባል ነዉ የሚል የፈጠራ ድርሰት መቅረቡ ነዉ። በአንጻሩ አንድን የህዝብ ባህላዊ ተቋም ፍትህ ሚኒስቴር (ጠቅላይ አቃቤ ህግ)በአዋጅ ከተሰጠዉ ስልጣን በመተላለፍና በደመኝነት መንፈስ አሸባሪ ብሎ መሰየሙ ነዉ። ፋኖ የአማራ ህዝብ ተቋም ሆኖ እያለ የፋኖ ስመራርና አባል የሆኑ ሰዎች አሸባሪ ናቸዉ ብሎ መክሰስ ህስቡን እንደህዝብ ከመክሰሱም በላይ ለአማራ ህዝብ ተቋሙ ያሳየዉ ንቀት የሚያረጋግጥ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። የአማራ ጠላት የሆነዉ ዘረኛዉ ስርአትም ይሁን በመሳሪያነት እያገለገለ ያለዉ ጠቅላይ አቅቤ ህግ ሊያውቁት የሚገባዉ ጉዳይ ቢኖር ሁሉም አማራ ፋኖ መሆኑን ነዉ። የእኔፋኖ መሆንም በቀጥታ ከአማራነቴ ጋር የተያያዘ ነዉ። ሲወርድ ሲዋረድ የመጣዉ መላዉ የአማራ ህዝብ እስካሁን ድረስ ምን አልባትም በጉዲፈቻና በሞጋሳ ከተሸጡትጥቂት የአብይ አህመድ ቡድን የሆኑ የካቢኒ አባላት ዉጭ ሁሉም አማራ ፋኖ እንደሆነዉ ሁሉ እኔም በፋኖነቴ አላፍርም እኮራለሁ እንጂ! ቄሮችና አባገዳዉ ወንጀል እንዳልሆነዉ ሁሉ ፋኖነትን መንካት በአንድ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ከመሆኑም በላይ ምንጊዜም ቢሆን በማንነቴ ላይ የሚመጣን ጥቃት እንደባንዳዎችና በጉዲፈቻ እንደተሸጡ የስራዓቱ (የብልጽግናቡድን )አባላት ዝም ብዬ ልቀበለው እንደማልችል በድጋሚ ላረጋግጥ እወዳለሁ።ፋኖነት ወንጀል ሳይሆን በክብር የሚሰዉለት አማራዊነት ነው።

2ኛ አማራን መክሰሱ የአማራ ባህል ፣ እሳቤ ፣ትውፊት፣ እሴቶች ... እንዲስፋፉና እንዲጎለብቱ ለማድረግ ተንቀሳቅሷል ይላል። ይገርማል! እንዴት ይህ የበታችነት መንፈስ ያጠቃዉ ሃይል ስቃይ ካልሆነ እንዴት ክስ ሊሆን ይችላል። እዮብ ''አማራ መልካም ባህርይ ያለዉ ፣የማስተዋል ተሰጥኦባለቤትበቀላሉ ይቅር የሚል በተረጥሯቸዉ እኩልነትና ፍትህን የታደሉ ናቸዉ።ሲል ይገልጸዋል።”አማራዎች አእምሮአዊ ተግባራዊ አራሾች፣ ጥብቅ ሃይማኖተኞችና መንፈሰ ጠንካሮች ናቸዉ።እንደብሄር ዋናዋና ስኬታቸዉ በዉትድርናና አስተዳደር ነው(ሌቪን 1965)።

ራያ ደግሞ በ1943 አማራን እንዲህ ሲል ገልጾታል “ጥሩ ባህርይና መልካም ቁመና ፣ደልዳላ ሰዉነት፣አርበኝነትና ጦረኝነት፣ከመጠን በላይ ኩሩ ፣ፍትህ ወዳድ፣እንግዳ ተቀባይ ፣ለጋስ፣ሩሩህና ታማኝ ሲሆኑ ቶሎ የመቆጣትና ነብር የመሆን ባህርይ ይታይባቸዋል ይላል።” በአጠቃላይ ባህልና እሴት አንድ ህብረተሰብ ወይም የማህበረሰቡ ቡድን ከሌላዉ ተለይቶ የሚታወቅበትን መንፈሳዊ፣ ቁሳዊ፣ ምሁራዊና ስሜታዊ ባህርያት ከእነሁለንተናዊ ምልዕነት ያካትታል። ባህል፣ስነጥበብ ስነጽሁፍና፣የአኗኗር ዘይቤን፣ ዕሴቶችን ፣እምነትና ልምዶችን ጭምር የሚይዝነዉ። ባህል አንድ ሰዉ በአጠቃላይ በማህበረሰቡ አባልነቱ የሚያገኘዉ ባህርይ፣እዉቀትና ክህሎት ነው(ዩኔስኮ 1982)።

ከዚህ አንጻር የአማራባህልና እሴቶች ለኢትዮጵያ ይሁን ለቀሪዉ አፍሪካዊ በረከት እንጂ እርግማኖች አይደሉም።ለምሳሌ አማርኛ የኢትዮጵያና የአፍሪካዉያን ሀገር በቀል()ቋንቋ ሲሆን የአማርኛ ፊደልደግሞ በአፍሪካ ብቸኛዉ በአለም ደግሞ ቅጥራቸዉ በአስር ከሚጠሩ ፊደሎች ዉስጥ አንዱ ነዉ። እንዲህ አይነቱ በረከት በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በአፍሪካ ሰማይ ስር እንዲስፋፋ ማድረግ ማንን ያስቀይማል።እዉነታዉ የራሳቸዉ ባልሆነ ታሪክ፣ቋንቋና ኢደል እንኩራ ብለዉ የሚሰቃዩ ጥቂቶችን ካልሆነበስተቀር መላ ኢትዮጵያዉያንና አፍሪካዉያን ቅር የሚያሰኝ አይሆንም።

የአማራ ባህል፣ እሴትና እሳቤ እንዲህ አይነት ሆኖ ሳለ የሚያስከስስቢሆን ኖሮ ከዚህ በከፋ መልኩ ለጌጣቸዉ የቆሙ በመምሰል ተወሰድንበት ያሉትን አካባቢ ባልተገባ መልኩ ሲገልጹ የሰንበቱትን የስረአቱ ቁንጮዎች ጥ%እቅላይ አቃቤ ህግ ለህግ ሲያቀርባቸዉ በተመለከትን ነበር። ምንም እንኳ እዉነቱ ሌላ ቢሆን” ዘመኑ የጎንደር ነዉ”ይህን እድል ሁለተኛ አታገኙትም።

”ዘመኑ የጀግናየኦሮሞነት ነዉ” ይህን ጊዜ ከእኛ ጎን ተሰለፉ ያሉት ሰዎች ዛሬ መገኛቸዉ እስር ቤት በሆነ ነበር።”ሰብረናቸዋል ፣ከአሁን በኋላ ከኦሮሞ ዉጭ ማንም ኢትዮጵያን እንዳይመራ አድርገናል፣ ትጥቃቸዉን ብቻ ሳይሆን ሱርያቸዉን ጭምር እናስወልቃለን”ያሉ ሁሉ መገኛቸዉ እስር ቤት በሆነ ነበር።

3ኛ ክሱ የፖለቲካ በመሆኑ አማራ ርስቱን ተቀምቷል፣ አማራ የህልዉና አደጋ ላይ ወድቋል፣ የምኖር ህልዉናዉ አልተረጋገጠም፣ በተለይም በኦሮሚያ ፣በቤንሻንጉል ጉምዝና በአዲስ አበባና ዙሪያዉ እንዲሁም በሊለኦች የኢትዮጵያ አካባቢዎች እየትፈናቀለ ፣ እየተገደለ፣ እየተሰደደ፣ እደተጨፈጨፈ፣ ሃብት ንብረቱን እያጣ፣የዘረኞች ጥይት ማብረጃና ጥቃት ሰለባ እንዲሆን ተደርጓል ይላል የሚል ክስ ቀርቧል። ነገሩ”ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድያፈራል”ካልሆነ በስተቀር የዚህ ስህተትና ጥፋተኝነቱ

ምኑ ላይ ነዉ። ሀገር አቀፍና አለም አቀፍ የሰባዊ መብት ድርጅቶች ተደጋጋሚ ሪፖርት ያወጡበት መንግስት ራሱ በትደጋጋሚ ያመነበት እዉነት አይደለም እንዴ? የቤጌ ምድር ህዝብ ለራሱ ርስት መሆን እንዴት ያንሰዋላ? ብሎ የቀላወለዉ ማን ነበር? በሀገርህ፣ በርስትህ፣ በማንነትህና በህልዉናህ እየመጡብህ ነዉ ያገኘሀዉን እየማረክና እየታጠክ ተዋጋና አድነኝ ሲል የንበርዉ ማን ነበር? ዘረኛዉ ስርአት ራሱን ከወንበሩ የሚያንገዳግደዉ በመጣ ጊዜ ከአማራ ጉያ ላይ ወድቆ የተማጸነዉ ከዚህ በላይ እንደተገልጸዉ ነበር። ራሱ የትደላደለ ሲመስለው ደግሞ የአማራን ህዝብ የፖለቲካ ጥያቄዎችን ጥፋትና ወንጀል አድርጎ ለክስ ማቅረቡ ተቀባይነት የሌለዉ መሆኑን ያመላክታል።

4ኛ የአቃቢ ህግ ዳኝነትን፣ ችሎትን ፣ ፍትህንና በአጠቃላይ የኢትዮጵያን ህዝብ የናቀ ክስ ነዉ። ማንኛውም ክስ ባቀርብ ጠያቂ የለኝም፣ ማንኛዉም አንቀጽ ብጠቅስ ማስፈጸም እችላለሁ በሚል ሃሳብ የተደራጀና አስገራሚ ጉዳዮች የተንጸባረቀበት መሆኑ የሚያስገርም ነዉ።

በአማራ ክልልም ይሁን በኢትዮጵያ ሲሪላንቃ የሚባል ቦታ የለም። አቃቢ ህግ እንዲህ ያለ ቦታ በመጥቀስ ከሰናል እዉነት እነዚህ አቃቢ ህጎች ኢትዮጵያዉያን ናቸዉ? 47ኛ ተከሳሽን በ2025 የፈጸመዉ ወንጀል በሚል ሊከሰዉ በመዝገባችን ላይ አይተናል። በእኛ መዝገብ ላይ 38ኛ ተከሳሽን ከ 54ኛ ተከሳሽ ጋር በመሆን ወንጀል ፈጽሟል ሲል ይገልጸዋል። ሆኖም በዚህ መዝገብ የተከለሉት 52 ሰዎች ብቻ ናቸዉ። እና ይህን ክስ ወይስ አሉባልታ እንበለዉ።

Ethio 251 Media

06 Feb, 11:15


ሰበር ዜና
ከ10,000(አስር ሽህ) በላይ አማራ የሆኑ ወታደሮች በአብይ አህመድ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ታስረዋል። በርካቶችም በየቀኑ እየተረሸኑ ነው።

ከ10,000(አስር ሽህ) የሚበልጡ የአማራ ልጅ የሆኑ ወታደሮች በአማራ ህዝብ ላይ ጭፍጨፋ እንዲፈጽሙ ቀጥተኛ ትዕዛዝ ተሰጥቷቸው ግዳጅ ቀጠና ላይ የነበሩ እና በሌሎች የሐገሪቱ አካባቢዎች የነበሩ ሲሆኑ ለአማራ ህዝብ እና ለፋኖ ከፍተኛ አቅም መፍጠር ተባባሪ ናችሁ የሚል ምክንያት የተነሳባቸው ሲሆን ከእስረኞቹ መካከል በመቶዎች የሚቆጠሩት በየ ቀኑ እየተረሸኑ ይገኛል።

የአብይ አህመድ ስርዓት ትክክለኛ አማራን ለማጥፋት የተቋቋመ መሆኑን ባለመገንዘብ ጠመንጃ ተሽከመው የአብይን ስርዓት ሲያስቀጥሉ የነበሩ እና ከእግረኛ እሰከ ከ ብርጌዳል ጀኔራል ድረስ ማዕረግ ያላቸው የአማራ ልጆች የአብይ አህመድ ቀጥተኛ ሰለባ መሆናቸው ሌሎች በመከላከያ ውስጥ ላሉ የአማራ ልጆች ሁነኛ ማስተማሪያ ነው።

በመሆኑም አማራ ሆናችሁ በመናጆ ሳንቲም ተታላችሁ መከላከያ ውስጥ ያላችሁ የአማራ ልጆች በሰዓቱ ፋኖን ከተቀላቀሉ ወንድሞቻችን ተምራችሁ በፍጥነት ፋኖን እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናቀርባለን ።

አብይ አህመድ ከህወሓት ጋር ጦርነት በገጠመ ጊዜ በርካታ የትግራይ ተወላጅ ወታደራዊ መኮንኖችን አስሮ ሲያሰቃያቸው እንደነበር ይታወቃል ።
ከዚህ ድርጊት ያልተማሩ የአማራ ልጆች መከላከያ ውስጥ ምን ይሰራሉ !?

በነገራችን ላይ የትግራይ ተወላጅ የሆናችሁ አሁን ክፍለጦር እና ሬጅመንት በመምራት ላይ ያላችሁ የጦር መኮንኖች አብይ አህመድ በፈለገ ጊዜ አስሮ ሲያሰቃያችሁ እንደነበር ዘንግታችሁ እሱ በፈለገ ጊዜ ፈቶ ንፁሐን ትገድሉ ዘንድ ወደ አማራ ክልል መጥታችሁ በማታውቁት እና በማይመለከታችሁ ጦርነት እየተሳተፋችሁ በመሆኑ ከዚህ ጨፍጫፊ ስርዓት ራሳችሁን እንድታገሉ እናሳስባለን ።

ሌሎች በመከላከያ ውስጥ ያላችሁ ደግሞ የአማራ ጥያቄ በሐይል እንደማይቀለበስ ተገንዝባችሁ የፋኖ ወንድማችሁን እንድትቀላቀሉ ጥሪ እናደርጋለን ።

አማራም ሆነ ኢትዮጵያ ነፃ የሚወጡት ህዝባዊ መንግስት ሲመሰረት እንጅ ከእንግዲህ በኋላ በኢትዮጵያ ምድር በታንክ ጋጋታ የሚፀና መንግስት እንደማይኖር ልናስገነዝባችሁ እንወዳለን ።

የአማራ ፋኖ በጎጃም በቀጣይ የሚያወጣውን የምህረት አዋጅ ተጠቅማችሁ የህልውና ፤ የነፃነት ፤ የእውነት እና የሐገር ክብር እና የሐገር ፍቅር ስሜት የሚያንገበግበውን የአማራ ፋኖን እንድትቀላቀሉ ስንል ከወዲሁ እናሳስባለን ።

አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
(የአማራ ፋኖ በጎጃም )

Ethio 251 Media

06 Feb, 09:18


የአዲስአበባ ማህበራዊ ንቅናቄ(አማን) እና አራዳ ተዋሀዱ!

ሁለቱ አዲስአበባ ላይ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት አደረጃጀቶች ተዋህደዋል። ሁለቱ አደረጃጀቶች ለየብቻ እንዲሁም በጥምረት ላለፈዉ አንድ አመት ገደማ በከተማችን በአዲስአበባ ላይ የተለያዩ ስራዎችን ሲሰሩ ቆይተዋል። እንደማሳያ በተለያዩ የከተማዋ ጎዳናዎች ላይ የተቃውሞ በራሪ ወረቀቶችን መበተን, ባነሮችን በተለያዩ ቦታዎች ላይ በመስቀል እንዲሁም፤ የገዥዉ ብልፅግና ቢሮዎች ላይ የማስጠንቀቂያ ፍንዳታዎችን በመፈፀም ያለፈዉን አንድ አመት ገደማ አሳልፈዋል።

ሆኖም ግን የአላማም ሆነ የግብ ልዩነት ባለመኖሩ እንዲሁም አዲስአበባ ላይ ያሉ የተበጣጠሱ ትግሎን ወደ አንድ አምጥቶ ጠንካራ የማህበራዊ ንቅናቄ ድርጅት መመስረት እንዳለበት በመታመኑ በሁለቱ ንቅናቄዎች በተደረጉ ሰፋ ያሉ ውይይቶች ወደ አንድ "አማንአራዳ" የተባለ የማህበራዊ ንቅናቄ ድርጅትነት እንዲመጡ ተደርጓል።

ሁለቱ ንቅናቄዎች ከተዋሀዱበት ጊዜ አንስቶ ጠንካራ ድርጅታዊ መዋቅርን ከመመስረት ጀምሮ በተለያዩ የአዲስአበባ ሰፈሮች መዋቅሮችን በመዘርጋት, ግብ እና አላማችውን በማጥራት የማህበራዊ ንቅናቄ እቅዶችን እንዲሁም የትግል ማንፌስቶን ከማውጣት ጎን ለጎንም የተለያዩ ስልጠናዎችን በመዉሰድ ድርጅታዊ ስራዎችን ሲሰሩ ቆይተዋል።

በመሆኑም ለመላዉ የአዲስአበባ ህዝብ እና አገዛዙን መታገል የሚፈልጉ ማንኛዉም ኢትዮጵያዊ ከአማንአራዳ ጋር በአጋርነት እንትቆሙ የትግል ጥሪ እናስተላልፍለን።
አማንአራዳ ማህበራዊ ንቅናቄ
ጥር/2017

Ethio 251 Media

05 Feb, 11:52


ሰበር ዜና!

የአገዛዙን ዙፋን ጠባቂ ሚሊሻ የወገኖቹ ግፍ ያንገፈገፈው ሚሊሻ በጥይት ነቅሷቸው ወደ ነበልባል ተቀላቀለ።

በትናትናው በዕለተ መድሓኒያለም በቀን 27/5/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:35 ገደማ አንድ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ አገዛዙ በግዳጅ አፍሶ አሰልጥኖ ያስታጠቀው ሚሊሻ በቆይታው የአገዛዙ አስከፊነት አንገፍግፎት ከአማራ አብራክ የወጡት የሚሊሻዎቹ በገዛ ወገኖቻቸው የሚያደርጉት ዘረፋ ፣ድብደባ፣ሴት ደፈራው አልቋቋም ብሎ አገዛዙን ትቶ ለመውጣት ቀን ሲያመቻች ቆይቶ ትናንት በተጠቀሰው ሰዓትና ቀን በአረርቲ ከተማ አረርቲ መለስተኛ ሆስፒታል ፊት ለፊት ባለ መጠጥ ቤት የአገዛዙ ሚሊሾች በመጠጥ ቤቱ የሚጠቀሙ ግለሰቦችን በግዳጅ ጋብዙን እያሉ ሲጋበዙ ውለው ሂሊናቸውን እስኪስቱ ጠጥተው የጋበዙዋቸውን ግለሰቦች በጋበዙ ሲደበድቡ የተረፋቸውን ገንዘብ በግዳጅ ሲቀበሉ አላስችል ያለው ጀግናው ሚሊሻ እንቢ በወገኔ ግፍ በማለት የያዘውን ክላሽ ከትከሻው አውርዶ መጠበቂያ ፈቶ ካታውን ፈልቆ ጥይቱን አቀባበለ ጀግናው ቆርጧል ዛሬ የወንድሞቼን ደም እበቀላለሁ ከራሱ ሙግት ገጠመ የጫካዎቹ ወንድሞቹ ናፈቁት ሌቦቹን ወሰነባቸው ጣቱን ከምላጭ አገናኘው የመጀመሪያውን ጥይት ከዚህ ቀደም የአርሶ አደር ግመል ፣እህል ከጎተራ በመስረቅ ከተወለደበት አካባቢ በእድር በተባረረው   የ አገዛዙ ሚሊሻ ላይ ሌባው ደረጀ ደስታ እሸቴ ማህል ግንባሩ ላይ አረፈች ። ደረጀ ወዲያው ምድርን ተሠናበት።

ጀግናው ደግሞ የክላሹን ምላጭ አባው ጥላሁን እሸቴ ላይ ነካካው አባው እና ደረጀ የወንድም አማች ልጆች በጀግናው ጥይት በጥቁር አስፓልት በቀይ ጥይት ተነድለው ወደቁ።

ጀግናው አሁንም በሌላኛው ሚሊሻ ላይ ተስፋዬ ሠለሞን ለይ ተኩሶ ከአቆሰለው በኋላ ወደ ወንድሞቹ አቅጣጫውን አዙሮ እዬተመናሸረ ብልፅግናን ትቶ ወደ አማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለ ጦር በቆፍጣናው በወንዶቹ ቁና ሃምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን የሚመራውን ነበልባል ብርጌድን ተቀላቀለ።

ሟች ሚሊሻ ደረጀ ደስታ ከዚህ ቀደም በአረርቲ ማርያም ቤተክርስታያን ግቢ አንድ ዳቆን ዮሐንስ (አጥላው) ተሾመ ተፈራን በግፍ የገደለ ወንጀለኛም ነበር።

በአገዛዙ ወንበር ጠባቂዎች ዛሬ መተማመን ጠፍቶ ትርምስ ነግሷል ሚሊሻው እርስ በርሱ አይጥና ድመት ሆኗል።

የወድም አማቾቹ ልጆች በአንድ ቀን ተቀብረዋል ።ሚሊሻ ተስፋዬ ሰለሞንም በአረርቲ ሆስፒታል በሞት አፋፍ ላይ እንደሆነ መረጃ ደርሶናል።

ነበልባልም ለሟቾች እንዲይ ሲል በግጥም ከዚህ ምድር እስከወዲያኛው ሸኝቷቸዋል።

=እንግዲህ እንዲህ ነው የባንዳ ውለታ፣
  አይ አባው ጥላሁን ደረጀ ደስታ፤

በጥይት ተቆልተው ሲኦል ስትጠብቅ በሮቿን ከፋፍታ፣
በጥይት ተቆልተው ተከታትለው ሄዱ ከማይቀረው ቦታ፤

እንግዲህ እንዲህ ነው የባንዳ ውለታ፣
አይ አባው ጥላሁን ደረጀ ደስታ፤
ሲኦል ስትጠብቅ በሮቿን ከፋፍታ፣
በጥይት ተቆልተው ተከታትለው ሄዱ ከማይቀረው ቦታ።

እምን ልግባ እያለ በሃሣብ ሲዋትት
አለማየሁ በላው በቀይ እርሳስ ጥይት፣
በጥይት በሳስቶህ ቁስለኛ ከምትሆን
ብትሞት ይሻል ነበር ተስፋዬ ሰለሞን፣

ዱላ ቆርጦ አይቀጣም እግዚኣብሔር ሲጣላ፣
የባንዳ ወላጆች ደስታና ጥላ፣
ጥላሁን ደስታ ወንድም አማቾቹ
አቤት ልጆቻቸው ለጥይት ሲመቹ፣

የአባው የደረጀ ዘመድም ወዳጆች
መልዕክት አስተላልፋ ለቀሩት ባንዳዎች።

ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ነፃነታችንን በክንዳችን!!!
አዲስ ትውልድ፣
አዲስ ተስፋ።

መረጃው/ የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር የነበልባል ብርጌድ ፋኖ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል ነው።

ፋኖ መ/ር አጥናፋ አባተ የነበልባል ብርጌድ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሃላፊ

   ጥር 28/5/2017ዓ.ም
           ነበልባሎች።

Ethio 251 Media

04 Feb, 15:51


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) የምስራቅ አማራ ኮር 1 ባለሽርጡ ክፍለጦር እና ኮር2 ታጠቅ ክፍለጦር አሃዶች በጋራ በሰሜን ወሎ ሀብሩ ወረዳ አንጦ ጨፌ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ፡፡

ዛሬ ጥር 27/2017 ዓ.ም በተደረገው ተጋድሎ የባለሽርጡ ክፍለጦር ሜካናይዝድ ክፍል 100% ኢላማዉን የጠበቀ የሞርታር ጥቃት በመፈፀም የፋሽቱን ስርዓት ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት የብልፅግና ሆድ አደር ካድሬ እንዲሁም ሆድ አደር ሚሊሻ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ሰርቷል::

በዚህም የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት መርሳ ከተማ ሆድ አደር አድማ ብተና እና ሚሊሻዎችን ለተሻለ ግዳጅ በሚል ጫካ ላይ ስብሰባ ጠርቶ የተሳሳተ ቅስቀሳ ፅንፈኛው ስለተዳከመ የቀጠናውን ሰላም መመለስና አካባቢውን ተረከቡ በሚል በመድረክ ሲደሰኩር የባለሽርጡ ሜካናይዝ ክፍል ወደ ስብሰባው ባስወነጨፈው የሞርተር ጥቃት የስርዐቱን ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ሆድ አደር ሚሊሻዎችና አድማ ብተና ሀይልን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ያሰቡትንም መድረክ ሳያሳኩ ስብሰባውን የበተኑት ሲሆን የሜካናይዝድ አጃቢ ሻለቃ በአንጦ ጨፌ የመጣውን ጨፍጫፊ ሀይል ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ወደ መጣበት እንዲመለስ አድርጎታል::

የታጠቅ ክፍለጦር አሃዶች ዙፋን አቦ ቀበሌ በመነሳት ከላይ ወደታች አጋምሳ እና ወረላሎን ማለትም ከመርሳ ከተማ ደቡባዊዩን አቅጣጫ አድማ ብተናና ሚሊሻ የሰፈረበትን ምሺግ በመስበር በርካታ ጠላት ሲደመስሱና ሲያቆስሉ ጠላት ነፍስ አውጭኝ ብሎ ፈርጥጧል::

የባለሽርጡን እና ታጠቅን በትር መቋቋም ያቃተዉ የባንዳ ጥርቅም የግለሰብን ሀብትና ንብረት እየዘረፈ፣ እያወደመና የዘወትር ልምዱ የሆነዉን ንፁሃንን ኢላማ ያደረገ ሞርታር ጥቃት በመፈፀም ሶስት ገበሬዎችን ሲገድል በተመሳሳይ ከግለሰብ ቤት ላይ በተወረወረ ሞርተር ሁለት እናቶች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰ ሲሆን እነዚህ እናቶች አሁን በህክምና ላይ ይገኛሉ፡፡

በቀጣይም መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
ጥር 27/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

04 Feb, 15:18


የአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለጦር ልጅ ስዩም ብርጌድ ከእንሳሮ ወረዳ ከሶስት ቀበሌወች በፍላጎት ወደ ትግሉ የተቀላቀሉ አባት አርበኞችን አሰልጥኖ አስመረቀ።
የአማራን ህዝብ የህልውና ትግል መቀላቀል አለብን ብለው ከእንሳሮ ወረዳ ሶስት ቀበሌወች ማለትም የትኖራና ቦለድ ቀበሌ፣ ቀንና ሞልታንባ ቀበሌ፣ካራምባና ጥቁርዱር ቀበሌወች ውስጥ የተውጣጡ በርካታ አባት አርበኞችን በአካል ብቃት ፣በወታደራዊ ሳይንስና ፣በፖለቲካ አሰልጥኖ የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች፣ የብርጌዱ አመራሮች፣የሃይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌወች በተገኙበት ተመርቀዋል።
ተመራቂ አባት አርበኞች የብልፅግናው ስርአት የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ ለማጥፋት የተሰለፈ ስለሆነ ሁላችንም በአንድነት መንፈስ በመተባበር ይህን የበሰበሰ ስርአት በማክሰም ህዝባችንን የሚመጥን ስርአት መትከል አለብን ሲሉ ተደምጠዋል።
ክብር ለተሰውት ሰማዕታት
ድላችን በተባበረ ክንዳችን

ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ
ጥር 27/2017ዓ.ም
ከአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል

Ethio 251 Media

04 Feb, 13:30


ከአገዛዙ ነፃ በሆነችዋ የቋሪት ወረዳ የቸሩ መድኀኔዓለም ዓመታዊ የንግሥ በዓል በድምቀት ተከበረ
═══════❁✿❁ ════════
(ጥር 27/2017 ዓ.ም፣ ነበልባሉ የገረመው ወንዳውክ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት)
በቋሪት ወረዳ ዋና ከተማ ገ/ማርያም የሚገኘው የደብረ ገነት ቋሪት መድኀኔዓለም ዓመታዊ የንግሥ በዓል ዛሬ በድምቀት እየተከበረ ነው።
ባሳለፍነው ዓመት ከተማዋ በጨፍጫፊው ሥርዓት እጅ ስለነበረች ወዳጅ ከወዳጁ፣ ወንድም ከወንድሙ ሳይጠያየቅ ክብረ-በዓሉ በደበዘዘ ድባብ ማለፉ የሚታወስ ነው።
በተለያዩ ጊዜያት ወደ ቋሪት ወረዳ የገቡ አራት የአገዛዙ ክ/ጦሮችን የዐማራ ፋኖ በጎጃም 5ኛ ክ/ጦር ነበልባሉ የገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ከወረዳው ማኅበረሰብ ጋር በመኾን እንደ ሳማ ለብልቦ በማስወጣቱ በዚህ ዓመት የከተማዋ ማኅበራዊ እሴት ተከብሯል።
በወረዳው የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ሊቃውንት ካህናት፣ መምህራን፣ ዲያቆናት፣ መዘምራን፣ አማንያን፣ ተገኝተዋል።
ሸሽተው የማያመልጡና አሯሩጠው የማይጨብጡ እናቶችና አባቶችም አካባቢያዊ የሰላም ስጋት ሳያሳስባቸው በዓሉን እያከበሩ ይገኛሉ።
የዐማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ የኔዓለም ዘለቀና ሌሎች የገረመው ወንዳውክ ብርጌድ አመራሮችም የኅብረተሰቡን ደስታ ለመካፈል በገበዘማርያም ከተማ ተገኝተዋል።
እስካሁን ከታዩ የንግሥ ክብረበዓላት ልዩ መሆኑንም አንዳንድ ተሳታፊዎች ተናግረዋል።

መላ የእምነቱ ተከታዮች እንኳን አደረሳችሁ!
🖍 መልካም ዐውደ-ዓመት
👉 ዓመት እስከ ዓመት ቸር እንሰንብት

Ethio 251 Media

03 Feb, 19:32


ልዩ መረጃ!

ነገ በቀን 27/5/2017 ዓ. ም የትግራይ ተወላጅ ሰላማዊ ሰልፍ የሚል በአዲስ አበባ ተዘጋጅቶ ነበር።

ከእያንዳንዱ ክ/ከተማ 100ሺ ሰው እቅድ የተሰጠ ሲሆን አጠቃላይ ከ11ዱም ክ/ከተማ ከ1ሚሊየን በላይ የትግራይ ተወላጅ ያልሆኑ የብልፅግና አባል እንዲያሳትፉ ተልዕኮ ተሰጥቶ በአቴንዳስ እየተመዘገበ ጥሪ እየተደረገ ነበር፣ የሰልፉ ዓላማ ጌታቸው ረዳን ቡድን የሚያወድስና የእነ ደብረፂዮንን ቡድን የሚረግም የተለያዩ ባነሮችና መፈክሮች ተዘጋጅተዋል።

ቢሆንም ግን የነገ የትግራይ ተወላጅ ሰልፍ የቀረበት ምክንያት:-

1. የትግራይ ተወላጅ እሽ ብለው ሊቀሩ ስለሚችሉ የማሳመንና በየቤቱ መዝግቦ በሰልፉ ያልተሳተፈ ስም ዝርዝራቸው ለፖሊስ እንደሚሰጥ በመንገርና እንዲፈሩ ለማድረግ ጊዜው በቂ ባለመሆኑ

2. የእኛን/ የብልፅግና አባላትን/ የትግራይ ተወላጅ አስመስሎ እንዲሳተፉ ለማድረግ ነገና ከነገ ወዲያ በየክ/ከተማው በአንድ ማዕከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ለመስራት

3. ሰልፉ ብልፅግና ያዘጋጀው እንዳልሆነና የትግራይ ተወላጅ ጥያቄ ጠይቀው መንግስት እንደፈቀደላቸው ተደርጎ ለተሳታፊዎች ማስገንዘብ አንዲቻል

4. የባነርና የተለያዩ ብሮሸሮች ዝግጅት በቂ ባለመሆኑ ጊዜ ያስፈልጋል በሚል ነው የተራዘመው

ስለሆነም ሀሙስ ሌሊት ከ10:30 ጀምሮ ከየቤታቸው በመኪና ተጭነው ወደ መስቀል አደበባይ ከላይ የጠቀስኩትን ቁጥር እንዲሳተፉ ይደረጋል ተብሏል

* ሌላው ህውሃት ከኤርትራ ጋር በመሆን ጦርነት ሊከፍትብን እየተዘጋጀ ነው የሚል ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ ገብተዋል።

Ethio 251 Media

03 Feb, 18:29


#ጅጋ_ሻለቃ አስደማሚ ኦፕሬሽን በማካሄድ ተሽከርካሪና የጠላት መካከለኛ አመራሮች ተቆጣጠረ‼️

የአማራ ፋኖ በጎጃም የራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም (5ኛ) ክፍለ ጦር አረንዛው ዳሞት ብርጌድ ጅጋ ሻለቃ  ከፍኖተሰላም ፣ከቁጭ ፣ከሽንዲ ፣ከቡሬና ከተለያዩ ከተሞች አገዛዙ የሰባሰባቸውን ወጣቶች ወደ ሁርሶ የስልጠና ማዕከል ለመውሰድ ጉዞ ላይ በነበሩበት ሰዓት ከጅጋ ወደ አዲስ አበባ መስመር
#ወንጌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ #አናብስቱ_ጅጋ_ሻለቃ ባካሄደው ሰርጂካል ኦፕሬሽን በሰልጣኞች ተሸከርካሪ መሀከል ቆርጦ በመግባትና ውጊያ በመክፈት 5 የመከላከያ አመራሮች አባላት ከእነ ተሽከርካሪያቸው ተማርከዋል።

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!

©ፋኖ ዮሴፍ ሀረገወይን የአፋጎ 5ኛ ክ/ጦር የሚዲያ ባለሙያ
           

Ethio 251 Media

03 Feb, 17:35


https://rumble.com/v6gixps--251-zare-february-3-2025-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

03 Feb, 16:08


በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ እናሸንፋለን ቀበሌ ንፁሃን አርሶ አደሮች ተረሸኑ

የአብይ አህመድ የጥፋት እጆች በአማራ ህዝብ ላይ እየተባባሰ እና ከእለት እለት ንፁሃንን በተገኙበት በየቤታቸው መረሸን የዕለት ተግባሩ አድርጎ ተያይዞታል።

የአማራ አርሶ አደርን ማዳበሪያና ዘር ከልክሎ የአማራን አርሶ አደር ዘርቶ እንዳያመርት የተሴረበት አርሶ አደር ዛሬ ላይ ደግሞ በህይወት እንዳይኖር ዘርፈ ብዙ ጭፍጨፋዎችን እያደረሰበት ይገኛል። ይህ ፋሽስታዊ መንግሥት የአማራውን የመንቀሳቀስ መብት ገድቦና መንገድ ላይ መንግስታዊ ሽፍታ አሰማርቶ በጅምላ እያሳገተ አማራውን በማንነቱ እንዲሰቃይ እያደረገ ይገኛል።

የአማራን እናት ሆድ በሳንጃ በመቅደድ አማራ አይወለድም የተወለደውንም እናጠፋዋለን በማለት ወደ አማራ ምድር ዘልቆ የገባው ጨፍጫፊ ሰራዊት ዛሬም ንፁሃን አርሶ አደሮችን በተወለዱበት ቀዬ በዕለተ አርብ ከየቤታቸው እያወጣ ረሽኗቸዋል።

ቃሉን በተግባር እያሳየን የሚገኘው የብርሃኑ ጁላ ጨፍጫፊ ሰራዊት አሁንም አማራ የሆነን ፍጡር ሁሉ በአማራ ምድር ደም ማፍሰሱን ቀጥሎበት በ 23/05/2017 ዓ.ም በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ሰሜን ሜጫ ወረዳ እናሸንፋለን ቀበሌ ልዩ ሰሟ ገሸር በመባል የመምትጠራ ቦታ አስር ንፁሃንን ከቤታቸው እያወጡ ረሽነዋል።

ስርዓተ ቀብራቸው ስነ ትናንት በ24/05/2017 ዓ.ም በገሸር ማርያም ቤተክርስቲያን የተፈፀመ ሲሆን ከባህር ዳር ተጉዞ ለለቅሶ የመጣን የሟች ወገን በለቅሶው ቦታ ላይ መግደላቸው ታውቋል።

በዕለቱ ከተረሸኑት መካከል ለጊዜው ስማቸውን ማወቅ የተቻሉት።

1. ተመስገን አለሙ
2. ጥሩየ ፀጋ
3. ምስጌ ፈጠነ
4. በቃሉዘመነ

ከባድ ቁስለኞች
1. በላይ መንጌ
2. ምትኬ ጥሌ
3. ፀጋ ሞላ
4. አትርሰው ተፈራ
5. ሙሉነህ ፈጠነ

Ethio 251 Media

03 Feb, 15:42


ከመብረቁ ተፈራ ብርጌድ መረጃና ደሕንነት የስለላ ቡድን የሞጣ ከተማ ሕዝብ ከአጭበርባሪዎች እንዲጠበቅ ያስተላለፈው መልዕክት!

በተለያዩ ከተሞች ጫት ቤት ተወዝፈው እየዋሉ በፋኖ ጀግኖች ስም ማሕበራዊ ሚዲያ ገጽ ከፍተው ገንዘብ የሚለምኑና የሚነግዱ አውደልዳዮች እንዳሉ የመብረቁ መረጃና ደሕንነት የስለላ ቡድን ባደረገው አሰሳ ደርሶበታል።

በመብረቁ ስም ከሚነገዱ ወንጀሎች መካከል የብርጌዳችን መስራችና ነባር ታጋይ እንዲሁም በቀድሞው አደረጃጀት የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ፋኖ በኋላም ጎጃም ዕዝ በአሁኑ አጠራር የአማራ ፋኖ በጎጃም የሆነውን ተቋም መስራችና አመራር በነበረው በጀግንነትና በክብር በተሰዋው ሻለቃ ተፈራ ዳምጤ ስም ለመለመን " ዳግማይ ተፈራ ዳምጤ ነኝ "የተፈራ ዳምጤ ታላቅ ወንድም" ነኝ" በማለት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጽ በመክፈት በጀግናው ጓዳችን ገንዘብ እየተለመነ እንደሆነ ደርሰንበታል። ልመናውም ፦ የተፈራ ዳምጤን ሐውልት ለማሰራት አስቤ ገንዘብ አነሰኝ አግዙኝ እያለ ከአረብ አገር ሴቶች ገንዘብ የሚሰበስቡ የከተማ አውደልዳዮች እንዳሉ ደርሰንበታል።

በጀግናውና በተከበረው በመብረቁ ስም ከሚፈጸሙ ወንጀሎች መካከል ሌላው ደግሞ የመብረቁን ስም ያጠለሹልኛል ሕዝብ ፋኖን እንዲያማርርልኝ ያደርጉልኛል ያላቸውን ሌቦች የሞጣ ከተማ ፖሊስና ሚሊሻ አደራጅቶ መከላከያ ፋኖን እየፈራ ከመሸ እንደማይንቀሳቀስ ከካምፕ እንደማይወጣ ስለሚያውቁ ፋኖም እንደ መከላከያ ከመሸ አይንቀሳቀስም ሌሊት ሞጣ አይገባም የሚል አሳማኝ ያልሆነ መረጃ በመያዝ ሞጣ ከተማ ሌሊት ቤት ለቤት እየዞሩ የግለሰቦችን ቤት እያንኳኩ መብረቁ ነን መብረቁ ነው የላከን ገንዘብ ክፈሉ በማለት አገሬ ሕዝቤ ተጨቁኗል ብሎ ለሕዝብ ነጻነት በወጣው በመብረቁ ብርጌድ ስም ፤ፖሊስና ሚሊሻ ያደራጃቸው ሌቦች የሞጣ ከተማን ሕዝብ ገንዘብ እየዘረፉት እንደሆነ የብርጌዳችን መረጃና ደሕንነት የስለላ ቡድን ደርሶበታል። በዚህም ከሕዝቡ በደረሰን ጥቆማ መሠረት ሌሊት ሞጣ ከተማ ባደረግነው አሰሳና ኦፕሬሽን በጨለማ ቤት ለቤት እየዞሩ በፋኖ ስም ሕዝቡን ሲዘርፉ የነበሩ የፖሊስና ሚላሻ ሌባ ወኪሎችን በኦፕሬሽን ይዘን ወጥተናል።

ሕዝባችን ፍርድ ተጓደለበት፣ ሕዝብ ተበደለ ብለን ነጻ ልናወጣው ጫካ የወጣንለትን ሕዝባችንን ሌሊት የሚዘርፉትንና በመብረቁ ስም የሚነግዱ የፖሊስና የሚሊሻ ወኪል ሌቦች ግን መቼም ቢሆን የማንፋታቸው ከጠላቶቻችን በላይ ጠላታችን ስለሆኑ ወንጀለኞችን ይዘን ለመቅጣት ከምንም በላይ አጽንኦት ሰጥተን የምንታገልለት ጉዳይ ሆኖ በውጭ አገር ያላችሁም ሆነ መላው የሞጣ ከተማ ሕዝብ ከላይ ከጠቀስናቸው ማጭበርበሪያ ዘዴዎች እራሳችሁን እንድትጠብቁ በተጨማሪም በመብረቁ ስም አጭበርባሪ ነጋጅ ሌባ ሲገጥማችሁም ለብርጌዳችን እንድታሳውቁ እናሳስባለን።

‹‹1 የ አማራ ፋኖ››
የአማራ ፋኖ በጎጃም ተፈራ ዳምጤ( 2ኛ) ክፍለጦር መብረቁ ብርጌድ መረጃና ደሕንነት ቢሮ

Ethio 251 Media

03 Feb, 15:40


ልዩ መረጃ!

የሐይማኖት አባቶች ሥርዓቱን አወገዙ!

በትናንትናው እለት ማለትም በጥር 25/2017 ዓ.ም በደብረ ኤልያስ ወረዳ ከሚገኙ ሁሉም አጥቢያዎች የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶች መንግስት በሰላም ማስከበር ሰበብ በእምነት ተቋማት ላይ እየፈጸመ ስላለው በደል ወደ ወረዳው ያመሩትን ከፍተኛ የመከላከያ አመራሮችና የወረዳ አመራሮችን ፊት ለፊት አነጋግረዋል።

ይህን ስብስባም የወረዳው ቤተ ክህነት የጠራው ሲሆን በዚህ ስብሰባም ጥሪ ተደርጎላቸው አጥቢያቸውን ወክለው የመጡ ከ60 በላይ ካህናት ፋኖን ደምስሼ ሰላምን አስከብራለሁ በሚል ሰበብ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት የወታደር ካምፕ እንዲሆኑ በማድረግ አብያተ ክርስቲያናት የእጣን ሽታ በሚሽትባቸው፤ ድምጸ ማህሌት በሚሰማባቸው መስዋእተ እግዚአብሔር በሚሰዋባቸው ፈንታ የመከላከያ የሲጋራ ሽታ እንዲሸትባቸው፤ የጥይት ደምጽ እንዲሰማባቸው፤ የወታደሩ የመጸዳጃ ቦታ እንዲሆኑና ማንኛውም ነውር የሆኑ ነገሮች እንዲተገበርባቸው የተደረገው ሳያንስ ጭራሽ ይባስ ብሎ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ በምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በደብረ ኤልያስ ወረዳ የሚገኘውን የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን ለማፍረስ እየሄደበት ያለውን አካሄድ አውግዘዋል።

ፋኖ ከከተማ እየተዋጋ ሳለ ገዳሙ ውስጥ የተቀመጠ ፋኖ አለ በሚል ሰበብ ገዳሙን ድጋሚ ለማውደም መሞከርም በጣም ስህተት ነው ብለዋል።አክለውም ከፋኖ ጋር ያላችሁን ጉዳይ በጀመራችሁት መንገድ ጨርሱ እንጅ ገዳሙ የመላው ኢትዮጵያውያን ገዳም ስለሆነ ገዳማችንን እንዳትነኩ ሲሉም አስጠንቅቀዋል።ስለ ገዳሙ የሚወራው የክስ ወሬም ራሱ መንግስት ገደሙን እንደበፊቱ ከሕዝብ አጣልቶ ለመምታት እየተጠቀመበት ያለ የፖለቲካ ቁማር እንጅ መሬት ላይ የሌለ ነገር መሆኑን ገልጸው ገዳሙ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቅዱስ ሲኖዶስ በምስራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት በደብረ ኤልያስ ወረዳ ቤተ ክህነት ከሚተዳደሩ ገዳማት አንዱ መሆኑን ካህናቱ ገልጸዋል።

በተያያዘ ዜናም ወራሪው ሰራዊት ገና ወደ ወረዳው ሲገባ የእመንባ ቅዱስ ጊዮርጊስን ቤተ ክርስቲያን እንደ ምሽግ በመጠቀም በቤተክርስቲያኑ ላይ ከፈጸመው ነውረኛ ወንጀል ባለፈ በአሁኑ ሰዓት አምስት አብያተ ክርስቲያናትን ለመሽግነት ስራ እየተገለገለባቸው ይገኛል ሲሉ ገልጸዋል።

እነዚህም
1/ አበሸብ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን
2/ የሳሰር አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን
3/ የቀጋት ኪዳነ ምህረት ቤተ ክርስቲያን
4/ ጽርሐ ጽዮን ጓይ ማርያም ቤተ ክርስታቲያን
5/ ምችግ ማካኤል ቤተ ክርስቲያን ናቸው

በእነዚህ አብያተ ክርስቲያናትም የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን በአግባቡ መፈጸም አለመቻላቸውን ምዕመናንም እንደልብ አምልኮ ለመፈጸም መቸገራቸውን ገልጸዋል።

እዚህ ላይ እኛም ቀደም ብለን ያናገርናቸው አገልጋዮችና ምዕመናን "ከብዙ ዘመን ጀምሮ አባቶቻችን ከውጭ ወራሪ ጠብቀው ያቆዩን ውድ የቤተ ክርስቲያን ንዋያተ ቅድሳቶቻችንና ቅርሶቻችን ህልውናቸው አደጋ ላይ ወድቋል" ሲሉ አብያተ ክርስቲያናቱና ቅርሶቹ በዚህ ጸረ ታሪክ አውዳሚ ቡድን የጥፋት ተልእኮ የተደቀነባቸውን የከፋ አደጋ ገልጸውልናል።

አክለውም መንግስት ለምን ይህን እንደሚያደርግ እንዲህ ሲሉ ነግረውናል። "መንግስት በአሁኑ ሰዓት እኒህን የእምነት ተቋማት ለምሽግነት እየተጠቀመ ያለው በአራት ምክንያቶች ነው።

1/ ፋኖ ወራሪውን ሰራዊት ለማጥቃት በሚከፍተው ውጊያ ከተቻለ በራሱ በፋኖ መሳሪያ ተቋማቱ እንዲወድሙ፤ ካልተቻለ ግን ራሱ የሽብር ቡድኑ አውድሞ ፋኖ አወደማቸው ለማስባልና ተቋሙን አውድሞና ፋ
ኖን ከህዝብ ለይቶ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ለመምታት፤
2/ በንጽህና አምልኮ የሚፈጸምባቸውን አብያተ ክርስቲያናት የሲጋራ ማጨሻ፤የመጸዳጃ፤እርስ በእርስ የመዳርያ(የወሲብ መፈጸሚያ) በማድረግ የተቋማቱን ክብር ዝቅ ማድረግ
3/ አገልጋዮቹንም ሆነ ምዕመናንን በማስፈራራት ካህናት አገልግሎታቸውን እንዳይፈጽሙ፤ምዕመናንም አምልኮ እንዳይፈጽሙ መሰናክል መፍጠር፤
4/ የአብያተ ክርስቲያናቱን የጥበቃ ሰራተኛ ጨምሮ ሕዝበ ክርስቲያኑን ከቤተ ክርስቲያን በማራቅ ተቋሙን ለዘራፊ አጋልጦ መስጠት ናቸው።

በጥቅሉ ይህ ፋሽስታዊ ሥርዓት እኒህና መሠል ነገሮችን በመፈጸም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማንትን ፈጽም ለማጥፋት እየተደረገ ያለ ሴራ ነው።" ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸውልናል።

እኛም ዘወትር ይህ ሥርዓት አንዱ ተልእኮው ነባር እምነቶችን ማጥፋት ነው የምንለው በምክንያት ነው።

ድል ለጭቁኑ ሕዝባችን!
ክብር ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተሰፋ

ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው
የአፋጎ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ/ ክፍለ ጦር የቀስተ ደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ

Ethio 251 Media

03 Feb, 15:15


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አምሓራ) ምዕራብ ወሎ ኮር ኢንጅነር ደሳለኝ አሰፋ መካነሰላም ክፍለ ጦር በመካነሰላም ግንባር ጀብዱ ተፈፀመ!

ሞት አይፈሬዎቹ የቦረና ሣይንት ጀግኖች በትናንትናው እለት ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም የአብይን ጥምር ጦር ሲያበራዩት ውለዋል::

ከመካነሰላም ከተማ ወጣ ብላ በሣይንት ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ቢሊ ተብላ በምትጠራው ታዳጊ ከተማ ግንባር በተደረገ እልህ አስጨራሽ ግብግብ በአርበኛ አብነው ታደሰ ምትኩ የሚመራው የኢንጅነር ደሳለኝ አሰፋ መካነሰላም ክፍለ ጦር ሰራዊት በጠላት ላይ የኃይል የበላይነት ወስዶ 3 አምቡላንስ አስከሬን ጠላት እንድታቀፍ አድርጓል::

በዚህ ትንቅንቅ አንድ ፋኖ በጀግንነት ሲዋጋ ቆይቶ መስዋዕትነት የከፈለ ሲሆን በአነስተኛ መስዋዕትነት የቦ/ሣይንት አውራጃ ጀግኖች ወሳኝ ወታደራዊ ድል አስመዝግበዋል::

የጦር ሰፈራቸውን ላለመልቀቅ ባደረጉት ትንቅንቅ ጠላትን አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ይዞታቸውንም ማስከበር ችለዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

"ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን"
ድል ለአማራ ህዝብ!
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
ጥር 26/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

02 Feb, 15:43


https://youtu.be/ipJQ2ms0icc?si=dpTegVJOvzYUWlC-

Ethio 251 Media

01 Feb, 15:57


ሰበር ዜና

የአማራ ፋኖ በወሎ /ቤተ-አምሓራ/ ምስራቅ አማራ ኮር1 በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የሚመራው ባለሽርጡ ክፍለጦር በሰሜን ወሎ ሀብሩ ወረዳ 024 ቀበሌ ልዩ ቦታው ጃራ በተባለ ስፋራ ታላቅ ድል ተጎናፀፈ፡፡

በተደረገው ድንቅ የደፈጣ ኦፕሬሺን የጊራናው ባለሽርጡ ክፍለጦር 3ኛ ሻለቃ የፋሽስቱን ስርዓት ወንበር ጠባቂ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል፡፡ በዚህም የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት የቀበሌውን ህዝብ ፅንፈኛውን አዳክመነዋል በሚል የሀሰት ፕሮፓገንዳ ለመንዛት ስብሰባ በሚል ሰበብ መነሻውን ድሬ ሮቃ በማድረግ ወደ ጃራ በፖትሮል የመጣውን የፋሽስቱ አብይ አህመድ ስልጣን ጠባቂና ጨፍጫፊ ሀይል ከነ ፓትሮሉ በመደምሰስ በርካታ ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል፡፡

በተያያዘም ከዙፋን ጠባቂው ሰራዊት ጋር አብሮ የራሱን ህዝብ ሊወጋ ከነበረው የሚኒሻ ሀይል 10 የሚሆኑት ከነትጥቃቸው ወደ ፋኖ ሀይል ተቀላቅለዋል፡፡ በዚህ ተጋድሎ የስርአቱን የፕሮፖገንዳ አጀንዳ ልታስፈፅም የነበረችን የስርዐቱን ካድሪ በቁጥጥር ስር ማድረግ ተችሏል፡፡

የባለ ሽርጦቹን በትር መቋቋም ያቃተዉ የባንዳ ጥርቅም የግለሰብን ሀብትና ንብረት እየዘረፈ፣ እያወደመና የዘወትር ልምዱ የሆነዉን ንፁሀን ላይ ኢላማ ያደረገ የሞርታር ድብደባ በመፈፀም በርካታ ንፁሃንን የሞት ሰለባ እያደረገ ይገኛል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
ፋኖ መምህር መሀመድ ሞገስ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) የባለሽርጡ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል
ጥር 24/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

01 Feb, 12:29


ሰበር የድል ዜና!

የአማራ ፋኖ በጎጃም የሶስተኛ ጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር በግዮን ብርጌድ እና ዘንገና ብርጌድ የትብብር ማጥቃት ትናንት አርብ ጥር 23 ቀን አመሻሽ ላይ የጀመረው ውጊያ እስከ ዛሬ ቅዳሜ ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም ቀን 7:00 ሰዓት ድረስ በተደረገ ውጊያ በወራሪው መከላከያ ላይ ሰዋዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሰናል።

በዚህም:- 1/ ሁለት የመከላከያ ሻለቃ አመራሮች ተደምስሰዋል
2/ 39 ( ሰላሳ ዘጠኝ) የሚሆኑት ተማርከዋል
3/ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁት እግረኞች ተደምስሰዋል
4/ ሶስት ተሽከርካሪዎች በአብሪ ጥይት ነደዋል ( ከጥቅም ውጭ ሆነዋል )
5/ 16 ( አስራ ስድስት ) ክላሽ ተማርኳል
6/ 8,000 ( ስምንት ሽህ ጥይት ተማርኳል ።

በውጊያው የግዮን ብርጌድ መብረቁ ሻለቃ እና ዘንገና ብርጌድ አስደማሚ የሆነ ጥምር ማጥቃት አድርገዋል ።

ተጨማሪ በቁጥር የበዛ ሰራዊት እና የጦር መሳሪያ ወደ ጎጃም በማስገባት እና የፋኖ አባል እና አመራር በገንዘብ በመግዛት ራሴን ከውድቀት እታደጋለሁ የሚል ዕቅድ የያዘው ጨፍጫፊ ስርዓት ነገን ከትናንት መማር ባለመቻሉ አጥፍቶ ለመጥፋት በድጋሜ እያሟሟቀ ነው።

ግብረ አበሮቹ ደግሞ የአማራ ክልል መንግስት ብለው የሚጠሩት ላይ እና ፌደራል መንግሥቱ ላይ ለመሰየም እያሟሟቁ ነው። ( በነገራችን ላይ ባለፉት 34 ዓመታት አማራ ክልል መንግስት ኖሮት አያውቅም )

አዲሱ ትውልድ በመስዕዋትነቱ ህዝብ እና ሐገሩን ለመጠበቅ እየተዋደቀ ነው።
አዲሱ አስተሳሰብ ከአማራ ህዝብ አልፎ ኢትዮጵያውያንን እና የሌላውን ዓለም ትኩረት እየሳበ ነው።
አዲሱ ተስፋ በጉጉት እየተጠበቀ ነው።

አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
( የአማራ ፋኖ በጎጃም )

Ethio 251 Media

01 Feb, 11:50


የድጋፍ አማራጮች !

ኢትዮ 251 ሚዲያን ለመደገፍ አማራጮችን ስትጠይቁን ለነበራችሁ ቤተሰቦቻችን ሁሉ !

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።


Bank Acct Info: Chase Bank
Account number
675535275
Routing number
322271627

Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

01 Feb, 09:39


የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) አዳዲስ ምልምል ሰራዊት አስመረቀ!

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ልጅ እያሱ ኮር ቤተ-አምሓራ ክፍለጦር በሚንቀሳቀስበት ቀጠና ለበርካታ ወራቶች ያሰለጠናቸዉን ፋኖዎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ::

ቤተ-አምሓራ ክፍለጦር በሞያቸው የካበተ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች ከእግረኛ እስከ መካናይዝድ ለወራቶች ያሰለጠናቸዉን በርካታ ምልምል ፋኖዎች በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል:: ተመራቂ ፋኖዎችም የአማራን ህዝብ ህልዉና ለማስከበር በቅንነትና በታማኝነት እስከ መጨረሻው የደም ጠብታ እንደሚፋለሙ ቃል እየገቡ ወደ ግንባር ገብተዋል::

የአማራን ህዝብ ህልዉና ለማስከበር በሚደረገው የፖለቲካ ትጥቅ ትግል በርካታ ዉጤቶች እየተመዘገበ ያለ ሲሆን ይህንን ዉጤት ለማስቀጠልና ትግሉን ለድል ለማብቃት ሰራዊቱን በሰው ሃይል ማጠናከርና ማብቃት ወሳኝ በመሆኑ ስልጠናዎችን አጠናክረን እናስቀጥላለን።

በመጨረሻም ይህንን የተሳካ ስልጠና እንድናደርግ ገንዘብ ብሎም ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደረጋችሁልን በዉጭም በዉስጥም ያላችሁ ወገኖቻችን በአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ልጅ እያሱ ኮር ስም እናመሰግናለን::

“ሰልጥነን እንዋጋለን፣ እየተዋጋን እንሰለጥናለን!”
"ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን"

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ልጅ እያሱ ኮር ቤተ-አምሓራ ክፍለጦር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ጥር 24/2017 ዓ.ም.

Ethio 251 Media

01 Feb, 08:57


"ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል!"
"ፋኖ ደጀን አለልኝ"

ፋኖ ደጀን አለልኝ ከአባቱ ከአቶ አለልኝ መለሠ ከእናቱ ወ/ሮ በለጡ መለሠ ጎንደር ከተማ ብላጅግ ሚካኤል ነው የተወለደው ። ፋኖ ደጀን የእነ ዘመነ አሰፍ ፣ ጓንቸ ውቤ ፣ እንዳልክ ደጀን ወንድም ነው አራቱም ጠላትን በሚገባ የቀጡ አንድ ቤተሠብ አንድ ሰፈር ነበሩ ነገር አገዛዙ የሚያደርሰውን በደል ለመመከት የሚገባቸውን ሁሉ በማድረግ ለአማራ ህዝብ በክብር ተሰውተዋል።

የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር የጃንታከል ብርጌድ አባል እና ስምሪት ከበርሀ መልስ የአዘዞ ድማዛ ብርጌድ ዘመቻ እቅድ ነበር።
ፋኖ ደጀን አለልኝ የአማራ ህዝብ በተለይ በጎንደር ከተማ የህልዉና ትግል አብሪ ኮከብ እና የትግላችን ማርሽ ቀያሪዉ ወደ ኋላ ማለት አማይወደዉ ፋኖ ደጀን አልኝ ትግልን የጀመረው በ18 ነበር። ደጀን ባለፉት አራት አመታት የሚጠበቅበትን ሁሉ ያደረገ የዚህ የህልውና ትግል በዕድሜ ትንሹ አርበኛ ነበር። ፍኖ ደጀን በጎንደር ከተማ በርካታ ባንዳ ጠላትን ፊት ለፊት የተጋፈጠ ጀግና ነበር። ፋኖ ደጀን ለአብነት ከተሠለፈባቸው ግንባሮች በጎንደር ከተማ በቆላድባ በአይንባ በጉራንባ በሽመላ ጋራ፣ በማሰሮ ደንብ በጣብላ፣ በአብራጅራ ፣በማሒን፣ በኮኪት በመተማ፣ በቋራ፣ በሽንፍ ግንባሮች ከእነ አርበኛ ናሁሰናይ አርበኛ ዘመነ አሰፍ አርበኛ ቻላቸው አርበኛ ታድሎ ጋር ተሰልፎ በርካታ የጠላት ሀይል የማረከ ጀግና ነበር ።

ፋኖ ደጀን በጎንደር ከተማ አይንባ ድርማ ቀበሌ ለጠላት የማይቀመሠው ጀግናው ደጀን ከአገዛዙ ጋር በጥቅም የተሣሠሩ ባንዳዎች በተኛበት ጥቃት ቢፈፀምበትም ፋኖ ደጀን አለልኝ ከጠላት ጋር አንገት ላንገት ተናንቆ ብዙ ባንዳዎችን እስከወዲያኛው ሸኝቶ በጀግንነት በሰርጎ ገብ ባንዳዎች መስዋዕትነትን ተቀብሏል።

ፋኖ ደጀን የህዝባችንን የዘር ፍጅት ለመከላከል አንድያ ህይወቱን ለመስጠት ዱር ቤቴ ብሎ ለአማራ ህዝብ ህልውና መጋረጥ በመረዳት ለትግሉ እውነተኛ ጀግና እና የነጻነት ታጋይ ነበር።

ጀግናዉ ፋኖ ደጀን አለልኝጠ በህልዉና ትግል ከ16 በላይ አዉደ ወጊያወችን በግንባር በመሠለፍ ያካሂደ ሲሆን በነዚህ አወደ ዉጊያወች ላይ በጠላት ላይ ቁሳዊ እና አካላዊ ቀዉስ አከናንቧል።

ጀግናዉ ፋኖ ደጀን ብዛት ያላቸዉን የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ አራዊቶችን አጋድሞ ዳግም እማትገኝ አንድያ ነብሱን ለተገፋዉ እና ለተጨቆነዉ ለአማራ ህዝብ ሰጥቶ አልፏል።

ደጀን ገና በልጅነት እድሜው ነበር መሣሪያ መክፈት ተምሮ እንዲሁም መንግስት ማለት ምን ማለት እንድሆን ገና በጧት እድሜው ነበር ታሪክን የተማረው። ደጀን በልጅነት እድሜው ለትምህርት ሲደርስ በጎንደር ከተማ በፈለጋ አቢዎት እና በፍሲለደስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታትሎዋል። ደጀን በሚኖርበት አካባቢ በጓደኞቹና በቤተሰቡ በጣም ተወዳጅ ነበር ። ደጀን ውድ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ነበር አይተኬ ህይዎቱን ለመስጠት ከ2008 ዓ.ም ጀምሮ እነ አርበኛ ዘመነ አሰፍ እና አርበኛ ናሁሰናይ ጋር ነበር ሀ ብሎ ትግል ሲጀምር ነበር ነፍጥ አንስቶ በተለያየ በቀጥታም ይሁን በተዛዎሪ ስለ አማራ ህዝብ ትግል የጀመረው። ደጀን በልጅነት እድሜው ስለጎንደር ብለው እስከ አዲስ አበባ በእግራቸው አገዛዙን በጠቅላይ ፍርድቤት ለመሟገት አንድ ወር በእግራቸው የተጓዙት የእነ አለሙ ተፈራ ዳኘው ተፈራ የኔው ንጉሴ ቤተሰብ ነው ደጀን በተወለደባት ቀበሌ በንጉሱ ዘመን የኢሀፖ መሥራች ከነበሩት ከነ ፀጋየ አለሙ ሀይለማሪያም አባተና ተፈራ ብርሀኑ ነበር የትግልን ባህሪ የተማረው ደጀን ነፍጥ ማንሳት የተማረው ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ወቅት ከዘመቱት ከቤተሰቦቹ የትጥቅ ትግል ባለታሪኮች ከእነ እንዳሄ አዳል የኔው ንጉሴና ብርሃኑ አለበል ነበር።

ደጀን ህይዎቱ የተሟላለት እያለ አልደፈርም አላስደፍርም የሚለው ወኔው ለአብሮ አደግ ጓዶቹ እና ቤተሰቡ ሁሌም በታሪክ ሲታወስ ይኖራል። ደጀን ጎንደርን አጠፋለሁ ብሎ የመጣውን ታጣቂ ሀይል የተወለደበትን ቀበሌ እና ጎንደርን ፊት ለፊት ከእን አርበኛ ቻላቸው እንየው ጋር በመሆን የተጋፈጠ ጀግና የቁርጥ ቀን ልጅ ነበር ። ደጀን የህውሃት ወራሪ አማራን ለማጥፍት በመጣበት ወቅት የፋኖ አደራጅ በመሆን ንቅናቄ በመፍጠር በርካታ ወጣቶች ወደ ትግሉ እንዲቀላቀሉና ስልጠና እንዲወስዱ ያደረገ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ነበር።

ደጀን ከህውሃት ጦርነት በኋላ የብልፅግና መንግስት በጥርጣሬ ይመለከተው ስለነበር በጎንደር ከተማ ከእነ አርበኛ ናሁሰናይ አንዳርጌ ኪሩቤል ክንዱ ሜጀር ጀነራል ውብአንተ አባተ አርበኛ ታደለ አንባቸው አርበኛ አይሸሽም ዮሐንስ በጎጃም ከደጋ ዳሞቱ ጀግና አርበኛ ታዱ አርበኛ መዝገቡ ጋር በመሆን እንዲሁም ዛሬ በህይዎት ካሉት ጀግኖች ጋር በመሆን በህውሃት ጦርነት የተሰውትን ጀግኖች እና በወሎ የተሰውትን እነ አርበኛ አሸናፊ አርበኛ ቻላቸው እንየው አርበኛ ሞላ ደስየ እና ሌሎች ጀግኖች በማስታወስ ትግላቸው ለማስቀጠል አማራጩ ነፍጥ መሆኑን በማመን ህይወቱ እስካለፈበት ድረስ ሲታገል ሲያደራጅ የጀግኖችን ትግል ያስተላለፈ ጀግና ነበር።

መስዋዕትነት መክፈል በትግል የማይቀርና የሚጠበቅ ሁናቴ ነው:: ታጋይ ይሰዋል ትግል ይቀጥላል:: በትግሉ ብዙ ጀግኖችን እየገበርን ብዙ ጀግኖች እየተተኩ በድል ዋዜማ ይገኛል:: ጀግናው ከለጋ እድሜው ጀምሮ ለህዝቡና ለሃገሩ ለከፈለው ዉድ ዋጋ ክብር ይገባዋል:: መስዋዕትነት የከፈለለትን አላማ ከግብ እናደርሳለን::

ደጀን ፀሀይ ዘቅዘቅ ብርሀኑዋን ስትነሳ ጠላት እንደማይደፍረው ያውቃልና ነገር ግን ከጎኑ አዕምሮዎቸው በጥቅም የተሞሉት እንደ ይሁዳ በገንዘብ ማንነትን የቀየሩ የዛን ጀግና ህይዎት እራትና ምሳ አብረው የበሉ ከጎንደር አርማጭሆ ከአርማጭሆ መተማ ቋራ ደንቢያ በእግር የተጓዙት ማንነታቸውን በመቀየር በተኛበት ተኩስ በመክፈት ዉድ አይተኬ ህይዎቱን ነጥቀውታል ።

ደጀን ግን ሞትን ንቆ ነበር ከቤቱ የወጣው። ደጀን የሚጠበቅበትን ሁሉ ለ60 ሚሊየን አማራ ካደረገ በኋላ ጀግናዉ እና የትግሉ ማርሽ ቀያሪ ጥር 21/2017 ዓ.ም ከጠላት ጋር አንገት ላንገት ተናንቆ በጀግንነት በ28 ዓመቱ መሰዋትነትን ተቀብሏል።

በመጨረሻም ጀግናው ደጀን የተሰዋለትን አላማ እንደሚሳካ አንጠራጠርም ስለከፈልክልን ሁሉ እናመሠግናለን!!

እግዚአብሔር ከደጋጎች ጎን ነብስህን ያሳርፍልን።

ድል ለአማራ ህዝብ

Ethio 251 Media

31 Jan, 15:42


ዛሬም ድሉ ቀጥሏል!

ጀግኖቹ የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ብርጌድ፣ የማቻክል በለይ ዘለቀ ብርጌድና የጎዛምኑ ጅበላ ሙተራ ብርጌድ ዛሬ ከቀኑ 5:00 ገደማ በደብረ ኤልያስ ከተማ በፈጸሙት የተቀናጀ ውጊያ በጠላት ላይ የተሳካ ጥቃት ፈጽመዋል።

አይኑ እያየ የእቶን እሳት በሆነችው ደብረ ኤልያስ ወረዳ ዘው ብሎ የገባው ራሱን ጥምር ጦር እያለ የሚጠራው የጠላት ሠራዊት አሁንም በጀግኖቹ ጥይት እየተገረፈ ይገኛል።

ዛሬም እርሱ ከተማውን ለቆ ወደ ገጠር ሲወጣ "እርሱ ወደ ገጠር ሲወጣ አንተ ከተማ ግባ..." በሚለው የአርበኛው መርህ መሠረት ጀግኖቹ ወደ ከተማ ገብተው በቀሪው ኃይል ላይ ውጊያ ከፍተው ክፉኛ ቀጥቅጠውታል።

በዚህ ውጊያ በርካታ ቁጥር ያለው የጠላት ጦር ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።

ገሚሱ ጠላት በአሁኑ ሰዓት ምችግ አፋፍ ላይ ሰፍሮ ይገኛል።ይህም ያንን መከረኛ ገዳም ከተቻለ በእገረኛ ካልተቻለ በሞርተርና በዙ-23 ለመደብደብ መሆኑ ግልጽ ነው።ለዚህ ድብደባ መሳካትም የወረዳ አስተዳዳሪ ተብየው አቶ ሃብታሙ እሱባለው የመከላከያ አመራሮችን በከፍተኛ ሁኔታ እየተለማመነ መሆኑ የመረጃ ምንጮቻችን ገልጸውልናል።

በተያያዘ መረጃ ጓይ የገባው የብልጽግና ቡድን መቶ የማይሞሉ ሠዎችን ሰብስቦ ፋኖ ሌባ ነው እያሉ ሲሰብክ ቆይቶ ስብስባውን ሳይጨርሱ አብሮ የገባው አድማ በትን ተብዮ የባንዳ ስብስብ ቁልፍ ሰብሮ በየቤቱ እየገባ የነዋሪዎችን ፍላት ቲሌቪዥኖችና ሌሎችንም የቤት ቁሳቁሶች ሲዘርፍ ውሏል።

ሕዝቤም የንግግራቸውንና ተግባራቸውን መቃረን ታዝቦ ስቆባቸው ተነስቷል።በዚሁ አጋጣሚ የተከበርከው የደብረ ኤልያስ ሕዝብ ሆይ በዚህ የእልህ አስጨራሽ ግብ ግብ ውስጥ እየከፈልከው ላለው ትልቅ መስዋትነት በብርጌዳችን ስም እጅግ እናመሰግናለን።

ድል ለሕዝባችን!
ድል ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተስፋ፣አዲስ አስተሳሰብ

ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው
የአፋጎ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር የቀስተ ደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ

Ethio 251 Media

31 Jan, 13:16


አርበኛ ዘመነ ካሴ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!

"እንኳን ለ85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር ክብረ በአል በሰላም አደረሳችሁ!

እንኳን 85ንቲ አገው ፊረስታኑ ማቢሪስ ታምፁናስ!!

ለአንድ ህዝብ የትናንት ታሪኩ ኩራት፥የዛሬ አብሮነትና ለነገ ተስፋውና ስኬት አመታዊ ክብረ በአላት ግዙፍ ትርጉም አላቸው።አመታዊ በአላትን በትኩረትና በምእላት ማክበር በትናንቱ ታሪኩና በዛሬ ማህበረሰባዊ አንድነቱ ጥብቀት የሚኮራ፥ ነገውን በህብረት ተስፋ የሚያደርግ ማህበረሰብ ለመፍጠር እጅግ ወሳኝ ነው።የአገው ፈረሰኞች ማህበር አመታዊ ክብረ በአል በዚህ ረገድ ሊጠቀስ የሚችልና የሚገባውም ነው።የአገው ህዝብ ኩሩ ታሪኩን ከሚያንፀባርቅቸው ውብ እሴቶቹ አንዱ ፈረሰኝነቱና ይህንም ለመዘከር በየአመቱ ጥር 23 ቀን በደማቁ የሚያከብረው የአገው ፈረሰኞች ማህበር ፌስቲቫል አንዱ ነው።ዘንድሮም ለ 85ኛ ጊዜ በደማቁ ይከበራል።ይህን የኩራታችን ምንጭ የሆነ ፌስቲቫል ዛሬ በደማቁ የምናከብረው ነገም ለመጭው ትውልድ ጠብቀንና አዳብረን የምናስተላልፈው ውብ ውርሳችን ነው!"

አርበኛ ዘመነ ካሴ
የአማራ ፋኖ በጎጃም ዋና ሰብሳቢ

Ethio 251 Media

31 Jan, 12:58


ደጋዳሞት ብርጌድ ከውጊያ ትንቅንቅ ባሻገር ሲገለፅ!!

የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ/(ተፈራዳምጤ) ክፍለጦር ደጋዳሞት ብርጌድ የታዱ አንተነህ ሻለቃ አባላት በትናንትናው ዕለት ማለትም ጥር 22/2017ዓ/ም ከግዳጅ መልስ በደጋዳሞት ወረዳ አቅላት ወይበኝ ቀበሌ ስር የሚኙ የአቅመ ደካሞችን ሰብል በማጨድ ህዝባዊነታቸውን  በተግባር አሳይተዋል።

አገዛዙና የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት የህዝባችንን ጉሮሮ ለማነቅ የአፈር ማዳበሪያ የከለከሉትን አርሶ አደር በአምላክ ቸርነት ሰብሉን አብቅሎ ለምን አጭዶ ከመረ ብለው በከባድ መሳሪያ ክምሩን በሚያቃጥሉበት በዚህ ወቅት ከህዝብ በህዝብ  ለህዘብ የወጣው ፋኖ ግን አንድያ ነፍሱን አሳልፎ ከመስጠት ጎንለጎን ማህበረሰባዊ አገልግሎቶችን በመስጠት በተደጋጋሚ ጊዜ ህዝባዊነቱን እያሳየ ይገኛል።

የአንድ ሸማቂ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም የአሸናፊነቱ ምንጭ  ህዝባዊ ደጀንነትና ህዝባዊነት መሆኑን የተረዳው ይህ ሸማቂ ትውልድ አገዛዙ እንደሚያደርገው ለታይታና ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ሳይሆን ከህዝብ ፍቅር በመነጨ አግባብ  የህዝብን ህመም በመታመም ከነፈዋሽ መድሀኒቱ አብሮ ተከስቷልና ሁሉም የዚህ ትግል ባለቤት መሰል የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴዎችን አጠናክረው ይቀጥሉ እንላለን።

አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ
ድል ለአማራ ፋኖ

አርበኛ ዳሞት አልኸኝ
የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ክፍለ ጦር ደጋዳሞት ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት!

Ethio 251 Media

30 Jan, 11:06


ሰበር ዜና!

ነበልባለቹ በኦሮምያ ክልል ኤጀሬ ገብተው የተሳካ ኦፕሬሽን ሰሩ።

የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ ተወርዋሪ ወደ ዋናው የአአ ናዝሬት ፈጣን መንገድ የሚያስኬሄደው አካባቢ ከቅርብ ርቀት እያዩት ወደ ኤጀሪ የሚሄደው በቆረጣ አልፈው መንገዱ በመዝጋት አናብስቶቹ ከሞጆ አቅጣጫ ወደ እጀሬ የሚሄደውን የተወሰኑት አንገት በመያዝ መንገዱን ሲዘጉ ቀሪዎቹ ከሞጆ ወደ ኤጀሬ አቅጣጫ ተምዘግዝገው ባስቀመጡት ደቂቃዎች ውስጥ በፍጥነት ወደ ከተማዋ በመግባት በከተማዋ የነበረው የአገዛዙ ዝፋን ጠባቂዎች ካምፕ እስከነ አሰስ ገሰሱ ዶግ አመድ በማድረግ ከተማዋ በቁጥጥር ስር አውለው አምሽቷል።

ይህን ተከትሎ በከተማዋ የሚፈለገውን ሆዳደር የከተማዋ ህዝብ ስያስለቅሱ የነበሩት ከየመወሸቂያቸውን እየተለቀሙ ተመጣጣኝ ቅጣት ተሰጥቷቸዋል።

በኦፕሬሽኑ ወቅት በጠላት ወገን በርካታ ሙትና ቁስለኛ ከመሆኑ በላይ ወደ ካምፕ ዘልቀው ሲገቡ በሬሳ ላይ እየዘለሉ እንደገቡ አናብስቶቹ አረጋግጠውልናል።

ይህ በንዲህ እንዳለ የአገዛዙ ሰራዊት ወደ ናዝሬትና ሞጆ በርካታ ሙትና ቁስለኛ ተሸክሞ የተጓዘውን አይሱዙና አምፕላንስ ያዩ የከተማዋ ነዋሪዎች ተጨማሪ ማስረጃ በማቅረብ አረጋጠውልናል።

ክንደ ብርቶቹ የነበልባል ብርጌድ ተወርዋሪዎች በጨበጣው ውግያ አንድ ጓድ ፋኖ ጌታሠው የግንባር ስጋ የነበረ ቆራጥ ታጋይ በነበልባል ብርጌድ ልዩ ተወርዋሪ በመሆን በርካታ ጀብዶችን በአገዛዙ ሰራዊት የፈፀመ ክንደ ብርቱ ነበር ትናንት በገባበት ግዳጅ በርካታ የአገዛዙን ወረበላ ሰራዊት የኦሮሚያ ሚኒሻና ልዩ ሀይልን በጨበጣ ተኩስ ሲያዝረበርባቸው ቆይቶ በጀግንነት ተሰውቷል ጀግና ይሞታል ስምና ትግሉ ይቀጥላል።

ይህንን ተከትሎ ከሞጆ ወደ ኤጀሬ የሚደረግ ማንኛውም የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ መቃረጡ ለማረጋገጥ ችለናል።

ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ

ክብርና ሞጎስ ለትግሉ ሰማእታት

ዘገባው የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ ሚድያና ኮምኒኬሽን ነው።

Ethio 251 Media

29 Jan, 18:51


ሰበር ዜና

የ802ኛ ኮር 58ኛ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በመቶዎች የሞቱበትና የቆሰሉበት ታላቅ ድል ተሰራ::

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ራያ ቆቦ ዞብል እና ራማ ድንጋይ ቀበሌ እና አዲስ ቅኝ አሳምነው ክፍለጦርና ሃውጃኖ ክፍለጦር ከባድ ትንቅንቅ ላይ ናቸው::

ከትናትና ጥር 20/2017 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ እስከ ዛሬ ጥር 21/2017 ዓ.ም ምሽት ድረስ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ በዞብል በኩልና በድንጋይ ቀበሌ በኩል በሁለት አቅጣጫ ወደ ራማ በብረት ለበስ በአራት ዙ23 እንዲሁም በሞርተርና መድፍ በመካናይዝድ ታግዞ የወጣ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በአሳምነው ክፍለጦር እና በሃውጃኖ ክፍለጦር ከባድ የፀረ ማጥቃት ዉጊያ ተሸንፎ አዲስ ቅኝ እና ጎለሻን አድርጎ ገሚሱ ወደ ራያ አላማጣ ዋጃ ከተማ እና ገሚሱ ወደ ራያ ቆቦ ጮቢ በር ፈርጥጧል::

የምስራቅ አማራ ኮር1 አሳምነው ክፍለጦር እና ሃውጃኖ ክፍለጦር በጋራ በሰሩት በዚህ ተጋድሎ የ58ኛ ክፍለጦር ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ በመቶዎች የሞቱበትና የቆሰሉበት ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል:: የቀድሞው 8ኛ ዕዝ የአሁኑ ሰሜን ምስራቅ ዕዝ 48ኛ 49ኛ እና 58ኛ ክፍለጦሮች እንዲሁም ከምስራቅ ዕዝ 12ኛ ክፍለጦርን ጨምሮ ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ሆነው ተበታትነው ያለቁበት ሁኔታ ነው ያለው::

በዚህ እልክ አስጨራሽ የሞት የሽረት ተጋድሎ በጀግኖቹ ተጋድሎ ያለዉን ሁሉ ተጠቅሞ ሽንፈት የገጠመው ጠላት እንደተለመደው ንፁሃንን ኢላማ ያደረገ የከባድ መሳሪያ ድብደባ እየፈፀመ ዉሏል:: ድንጋይ ቀበሌ አዲስ ቅኝ እና ኮባ ቀበሌዎች በከባድ መሳሪያ በሰው ህይወት በእንስሳቶችና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል:: ከዚህ ጋር ተያይዞም ከራያ ቆቦ ሮቢት በምዕራብ በኩል ባሉ የገጠር ቀበሌዎች ንፁሃንን ኢላማ ያደረገው የከባድ መሳሪያ ድብደባ ሲፈፀም ዉሏል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
ጥር 21/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

29 Jan, 17:39


የዛሬ ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-

https://twitter.com/i/broadcasts/1ynJODlllYExR

https://rumble.com/v6eq9j7--251-zare-january-29-2025-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

29 Jan, 16:30


በቋሪት ወረዳ የፋኖ ጊዜያዊ አስተዳደር ከቀበሌ የጎበዝ አለቃዎች ጋር በቀጣይ ዕቅዶች ዙሪያ ምክክር አደረገ!
═══════❁✿❁ ════════
ጥር 21/2017 ዓ.ም
የዐማራ ፋኖ በጎጃም 5ኛ ክ/ጦር ነበልባሉ የገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ጊዜያዊ አስተዳደር በቋሪት ወረዳ ከቀበሌ የጎበዝ አለቃዎች ጋር በቀጣይ ዕቅዶች ዙሪያ ምክክር አደረገ።

ነበልባሉ የገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና አስተዳዳሪ አርበኛ ይበሉ ጌታቸው ትግሉን በላቀ ፍጥነት ለመምራት ማኅበረሰቡ ሁሉን አቀፍ ድጋፋን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

ዋና አስተዳዳሪ አርበኛ ይበሉ አክለውም ነበልባሉ ገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ወረዳዉን ሙሉ በሙሉ ከጠላት ነፃ በማድረጉ ማኅብረሰቡን በአግባቡ እንዲያገለግሉ ለየቀበሌ አመራሮች መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
አልፈው አልፈው የሚታዩ የፀጥታ ችግሮችን በተባበረ ክንድ ማስቆም እንደሚገባ የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪው የፀጥታ ችግር በሚፈጥሩ ግለሰቦች ላይ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቀዋል።

ከተዋጊው ባላነሰ መልኩ ተዋጊዎችን እና መላ ሕዝባቸውን ያለደመወዝ ለሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎች ደመወዝ እስከሚለቀቅላቸው ጊዜያዊ መፍትሔ እንዲሰጥ አስተዳዳሪው በውይይቱ ላይ አሳስበዋል።

ነበልባሉ የገረመው ወንዳውክ ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት

Ethio 251 Media

29 Jan, 16:22


ድሉ ዛሬም ቀጥሏል
************
እርም የለሹ የመከላከያ ሰራዊት ዛሬም እንደ ልማዱ በቀስተ ደመና ፋኖዎች ጥይት ሲቆላ ውሏል። አማራን አጠፋለሁ ብሎ የሞት መልእክተኛ በመሆን እንደ እብድ ውሻ የሚልከፈከፈው የብርሃኑ ጁላ ጦር ጥፋቱ ወደራሱ ተመልሶ በቆረጠው ብትር እየተገረፈ ይገኛል።

በዛሬው እለትም ከትናንት በስተያ የተመታው ቁስሉ ሳይደርቅ ሀዘኑ ሳይጠፋ ደሜን እመልሳለሁ ብሎ በጨለማ ተጉዞ ፋኖን ለመክበብ ኃይሉን በሁለት አቅጣጫ ኃይሉን አሰማርቶ አድሯል።ይህም ጎፍጭማ ላይ የነበረውንና ከተማ የነበረውን ኃይሉን ሰብስቦ በማርዘነብና በየግዳድ ቀበሌዎች አሰማርቶ ፋኖን ለማፈን ሞክሮ ነበር።

ይሁን እንጅ የጠላትን እንቅስቃሴ እቅድ አስቀድመው ያጠኑት ጀግኖቹ የቀስተ ደመና ፋኖዎች ያደሩበትን ቦታ ለቀው ደፍጠው አደሩ።ከዚህም በኋላ ፋኖን አገኛለሁ ብሎ ዘሎ ከየግዳድ ትምህርት ቤት የገባውን የጠላት ኃይል አንበሶቹ የቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎችና የማቻክል በላይ ዘለቀ ብርጌድ ፋኖዎች ከበው ይወቁት ጀመር።

በተለይም የቀስተ ደመና ብርጌድ ተወርዋሪ የሆነችው ኃይል ከጠላት ምሽግ ሰብራ በመግባት ጠላትን ረፍርፋ ሙትና ቁስለኛውን አሳቅፈው ወጥታለች።
እስካሁን ባላን መረጃ መሠረትም 30 የጠላት ኃይል እስከ ወዲያኛው ሲሸኝ ከ35በላይ ቁስለኛ ሆኗል።በዚህ ከበባ ውስጥ ሆኖ ሲወቀጥ የነበረው የአራዊት ጥርቅምም ወደ አለቆቹ የድረሱልኝ ጥሪውን ያስተጋባ ጀመር።

በዚህ ሰዓትም በማር ዘነብ የወጣው የጠላት ኃይል በፍጥነት በመመለስ ዙ-23ቱንና ሌላውን ኃይል ጭኖ ደርሶለት ከመሉ መደምሰስ ታድጎታል።የቀስተ ደመና ጀግኖችም በሳልስት ቀን ልዩነት ድጋሚ ድልን ሲያጣጥሙ አምሸተዋል።

ለደብረ ኤልያስ ተብሎ ተመርጣ የመጣችው ራሷን የምድር ዶሮን እያለች የምትጠራው 32ኛ ክፍለ ጦርም የቀስተኞቹ የውጊያ ቴክኒክና ጥበብ ከአቅሟ በላይ ሆኖባት ይሄው በየሜዳው እንደ ቅጠል እየረገፈች ትገኛለች። በአሁኑ ሰዓትም ጠላት ሠራዊቱን ይዞ ወደ ኋላ ተመልሷል።

ድል ለተገፋ ሕዝባችን!
ክብር ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!

ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው
የአፋጎ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር የቀስተ ደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ
ጥር 21/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

29 Jan, 15:06


የአማራ ፋኖ በጎጃም ጃዊ መተከል (4ኛ) ክ/ ጦር የነጋሽ ብርጌድ፣የኤፍሬም ብርጌድ እና የደጀን ብርጌድ በቀጠናዊ ትስስር የተሃድሶ ፕሮግራም አካሄዱ።

በቀን 20/05/2017 ዓ.ም ሶስቱ ብርጌዶች ጥምረት ወይም ትስስር በማድረግ አንድነትን በማጠናከር ጠላትን የማዳከም እና የመደምሰስ ስራ እንደሚሰሩም ተገልጿል። የብርጌዶች ትስስር አጠቃላይ ለማህበረሰቡ ትስስር እና አንድነት መሰረት ነዉ ሲሉ የፕሮግራሙ ታዳሚዎች አስተያየታቸውን ተሰጥተዋል ።

በህዝባዊ ማዕበል የተጀመረው ትግል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየዘመነ ወደ ወታደራዊ መዋቅር እየተሸጋገረ በዘመናዊ ትጥቅ እና ወታደራዊ ስልጠና እየታገዘ በልዩ ልዩ የዉጊያ ስልቶች በመታገዝ ከሽምቅ እስከ መደበኛ ዉጊያ እየተደረገ የ4ኛ ክ/ጦር በጠላት ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሰ ይገኛል። ይህንን የአንድነት ገመድ በማስረዘም ብርጌዶችን በማስተሳሰር ጠላትን በተለያዩ ወታደራዊ ኦፕሬሽኖች ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናጠፋዋለን የሚሉ አስተያየቶችም ተሰጥተዋል።

የመንግስት ስርዓት በሚሰራው የከፋፋይነት ሴራ አገዉ እና አማራ በማለት እርስ በርሳችን ለማዋጋት የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ እየነዛ የሚገኝ ቢሆንም እኛ የአገዉኛ ቋንቋ ተናጋሪ አማራዎች ግን የአገዛዙን የከፋፋይነት እና የእርስ በርስ የመጠፋፋት ሴራ ስለተረዳን አንድነታችንን አጠናክረን ከፋኖ ጎን በመሰለፍ ይህንን ወንበዴ የመንግስት ስርዓት ማስወገድ አለብን ሲሉ የአገዉኛ ቋንቋ ተናጋሪ የአማራ አገዎች ተናግረዋል።
አዲስ ትዉልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
ከአማራ ፋኖ በጎጃም ጃዊ መተከል (4ኛ) ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃለፊ
ያዕቆብ ጌታሁን

Ethio 251 Media

28 Jan, 16:48


https://twitter.com/i/broadcasts/1lDGLlzyPNMGm

Ethio 251 Media

28 Jan, 16:31


ሰበር ዜና

አሳምነው ክፍለጦር፣ ሃውጃኖ ክፍለጦር እና ካላኮርማ ክፍለጦር ራያ ቆቦ ላይ ጠላት በመቶዎች የሞተበትና የቆሰለበት ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ምስራቅ አማራ ኮር1 አሳምነው ክፍለጦር እና ሃውጃኖ ክፍለጦር በጋራ ራያ ቆቦ ዞብል ከተማና ዙርያው ላይ ዛሬ ጥር 20/2017 ዓ.ም ንጋት ጠላት በተኛበት በተጀመረ ከባድ ዉጊያ በመቶዎች የሚቆጠር ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ ሆኗል:: ሁለቱ ክፍለጦሮች ሁለት ሁለት ሬጅመንቶችን በመጠቀም ቀሪዉን ቦታ በመሸፈንና ተጠባባቂ አድርገው ባደረጉት ተጋድሎ ታላቅ ድል ተቆናፅፈዋል::

በተጋድሎው ጠላት ከበባ ዉስጥ ገብቶ ብረት ለበስና ዙ23 መጠቀም እንዳይችል ሆኖ ቀዩ ጋሪያ ላይ ተዘግቶ እየተመታ ባለበት ሁኔታ ዞብል ከተማና ዙሪያዉን ኢላማ በማድረግ ቆቦ ከተማ ሆርማት በሚወነጨፍ 122 በሚባል መድፍ ንፁሃን ህዝብ ላይ እንስሳቶችና ንብረት ላይ ከባድ ጉዳት አድርሷል::

ከዚሁ ዉጊያ ጋር በተያያዘ ጠላት ዞብል ላለው ሃይሉ ተጨማሪ የሰው ሃይልና ንብረት እንዳይጨምር ለማድረግ ሮቢት ከተማ ላይ በተደረገ ወሳኝ ዉጊያ ምስራቅ አማራ ኮር2 ካላኮርማ ክፍለጦር ከጎብየ እስከ መንጀሎ ቀጠና በመሸፈን አመርቂ ድል አስመዝግበዋል::

ካላኮርማ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ መንጀሎ 2ኛ እና 4ኛ ሻለቃ ሮቢት ከተማ ሙሉ ለሙሉ 3ኛ ሻለቃ አሚድ ዉሃ ላይ በመዝጋት ጠላት ከወልድያና ሐራ ለዞብሉ ሃይል ተጨማሪ ሃይልና ንብረት እንዳይጨምር በማድረግ ታላቅ ተጋድሎ ያደረጉ ሲሆን ካላኮርማ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ መንጀሎ ላይ ሶስት ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ከነ ሙሉ ትጥቃቸዉና 1000 የክላሽ ተተኳሽ ማርከዋል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ)
ጥር 20/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

28 Jan, 15:42


ኦፕሬሽን ብስቁልል!

የደቡብ ወሎ ዞን የተለያዩ ወረዳዎች ማለትም ለጋምቦ፣ ከላላ እና ወግዲ ወረዳዎች አዋሳኝ የሆነችው ብስቁልል ላይ የተፈፀመው ልዩ ኦፕሬሽን!

ሰሞኑን በተደራራቢ ስራዎች እና በጊዜያዊ የኮሙኒኬሽን ክፍተት ምክንያት አንድ አስደናቂ መረጃ ሳናደርሳችሁ ቀርተን ነበር። በዋርካው ምሬ ወዳጆ የሚመራው የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አምሐራ) ሰራዊት ታሪክ መስራቱን ቀጥሎ በምዕራብ ወሎ ቀጠና በያዝነው ወር የመጀመሪያው ሳምንት መጨረሻ አካባቢ ምዕራብ ወሎ ውስጥ ጀብዱ ተፈፅሟል።

ጥር 6 ለ7 ሌሊት ወደ ለጋምቦ፣ ወግዲ እና ከላላ ወረዳዎች አዋሳኟ ብስቁልል ቀጠና ያቀናው ከ4 ወረዳዎች የተውጣጣው በርካታ የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ብስቁልል ላይ የምዕራብ ወሎ ኮር አዛዥ አርበኛ አደም አሊ ያለበትን ስፍራ ከቦ ቢያድርም ከሌሊቱ 10 ሰአት እስከ አመሻሽ ድረስ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ጠላት ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዶ በርካታ ኃይሉን አጥቷል።

የአርበኛ አደም አሊ የቀድሞ አጃቢ የነበረውና ከድቶ ወደ አገዛዙ የገባው አቶ ሰይድ አማረ የተባለ ግለሰብ ከወግዲ ወረዳ ድረስ ጠላትን እየመራ በደማሲቆ ካቢ በኩል አድርጎ ወደ ብስቁልል ሲገባ ከለጋምቦ አቅጣጫም በርካታ ጠላት ወደ ስፍራው አቅንቶ ነው ከባድ ጦርነት ሲካሄድ የዋለው።

በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ጠላት 10 ንፁሓንን የረሸነ ሲሆን ከወግዲ በኩል ከመጣው የጠላት ኃይል ብቻ 17 ወዲያው ሲደመሰስ 13 ቁስለኛ ወደ ሆስፒታል መግባቱ ተረጋግጧል።

ከለጋምቦ በኩል ከመጣው ጠላትም ከወግዲው ቁጥር ያላነሰ እንደተቀነሰለት የተገለፀ ሲሆን ጊምባ ከተማ ካለው የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 801ኛ ኮር የምዕራብ ወሎ ቀጠና ጊዜያዊ ማዘዣ ጣቢያ አቅራቢያ ብቻ 20 ወታደሮች ተቀብረዋል ሲሉ የሰራዊቱ የውስጥ ምንጮች ተናግረዋል። አቀስታ እና ገነቴ ደግሞ ስንት እንደቀበረ እራሱ በሁለቱ ከተሞች ውስጥ ያለው ጠላት ቢናገር የተሻለ ይሆናል።

አስከሬን እና ቁሰለኛ ከደህናው ጋር ቆጥሮ ሰራዊቱን ኦዲት አድርጎ ቀላል የማይባል ቁጥር ያለው ጓድ መጉደሉ ሲገባው በአምስተኛው ቀን ወደ ብስቁልል ተመልሶ የገባው ጠላት የ6 ወታድሮችን እግር በየጥሻው ማግኘቱን ነው የአይን እማኞች የተናገሩት።

ውጊያው በተደረገበት እለትም 6 አምቡላንሶች ወደ ቀጠናው ገብተው የጠላት አስከሬን ያነሱ ሲሆን ቁስለኞች በአንድ ኦራል ተጭነው ስለመወሰዳቸውም አርበኛ አደም አሊ ከአርሶ አደሮች መረጃ ደርሶት በማግስቱ ለሚዲያዎች ማረጋገጫ ሰጥቷል።

ኦፕሬሽን ብስቁልል በድምሩ ከ60 ያላነሰ የጠላት ኃይል የተመታበት ልዩ ኦፕሬሽን ሲሆን በወገን በኩል ደግሞ የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ስራ አስፈጻሚ የሆነው ኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው በርካቶችን ጥሎ ጀብዱ በመፈፀም በስተመጨረሻ መስዋዕትነት ከፍሏል።

ኮማንዶ ተመስገን ከአርበኛ አደም አሊ ጎን ሆኖ በጀግንነት ተፋልሞ ጠላትን አፈር አስግጦ ነው መስዋዕትነት የከፈለው። 

ፊት ለፊት ሲዋጉ ቆይተው ከበባ ሰብረው እና ጠላትን ከምሽጉ ነቅለው በማስፈርጠጥ ታላቅ ገድል እየፈፀሙ ባሉበት ቅጽበት በድንገት የተመታው ኮማንዶ ተመስገን በጥቂት መስዋዕትነት አስገራሚ የሚባል ጀብዱ የተፈፀመበት የኦፕሬሽን ብስቁልል አብሪ ኮኮብ ሆኖ ፊት ለፊት ተዋግቶ ሲያርፍ ጓዶቹ በአርበኛ አደም አሊ መሪነት ጦርነቱን ቀጥለው ጠላትን በታትነው የኮማንዶውን አስከሬን እና ትጥቅም አንስተዋል፤ አስከሬኑም በክብር እንድያርፍ ተደርጓል::

ጠላት አስከሬን ላለማስነሳት ደጋግሞ ከባድ መሳሪያ ቢተኩስም አርበኛ አደም አሊ ወይ ፍንክች በማለት በቦንብ ጠላትን በታትኖ በርካቶችን ገደል እንደከተተታቸው ነው ለማረጋገጥ የቻልነው።

ሰማዕቱ ጀግና ኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው ከሁለት ወር በፊት ወደ ትግሉ ሜዳ የመጣ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ በግል ስራ በመተዳደር ላይ ሳለ እንግዲህ ለህዝቤ ልሙት ብሎ በመወሰን የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦርን መስርቶ ትግሉን እንደጀመረና የክፍለ ጦሩ አደራጅ ኮሚቴ አመራር እንዲሁም ስራ አስፈጻሚ መሆኑ ይታወቃል።

በመሐል ሳይንት ወረዳ ውስጥ ተወልዶ ያደገው ኮማንዶ ተመስገን ለአማራ ህዝብ ሲል ውድ ህይወቱን በመስጠት ለቀሪዎቻችን ከባድ አደራ ሰጥቶን አርፏል። የእሱን አደራ እና መስዋዕትነት ሳንረሳ እኛም ተመሳሳይ ታሪክ በደማችን እየጻፍን በህዝባችን ላይ የተደቀነውን የህልውና አደጋ እንቀለብሳለን::

ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለትግል ጓዶቹ መጽናናትን እንመኛለን።

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ- አምሓራ) ምዕራብ ወሎ ኮር
ጥር 20/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

28 Jan, 15:36


በአማራ ፋኖ በጎጃም በበላይ ዘለቀ8ኛ ክ/ጦር በደባይ ጮቄ ብርጌድ #የዘመቻ_ዮሀንስ_አለማየሁ  ስም ከሰሞኑ ከወራሪው የጉጅሌው የነብርሀኑ ጁላ ጦር ኃይለኛ የሆነ ትንቅንቅ ተደርጓል።

ይኸውም በቀን ጥር 18 ለ19 /2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሲሆን መነሻውን ከቁይ ከተማ በማድረግ ወደ ደባይ ጮቄ ብርጌድ የጀረምስ 2ኛ ሻለቃን ለማጥቃት የተንቀሳቀሰው የጉጅሌው የብርሀኑ ጁላ ጦር  አይበገሬዎቹ #የደባይጮቄ_ብርጌድ ፋኖ አካል የሆነችው #የጀረምስ_2ኛ _ሻለቃ ጠላት የመጣበትን አቅጣጫ ፈጥና በመዝጋትና ቀድማ መብረቃዊ ጥቃት በመክፈት ልማደኛውን የዘራፊ የአብይ አህመድ ወንበር ዙፋን አስጠባቂ ቡድን በማበዳየት ሙትና ቁስለኛውን በማስታቀፍ ወደመጣበት አስፈርጥጣ ሸኝተዋለች!!!

በመቀጠልም ከስህተቱ የማይማረው ዘራፊው መከላከያ ሰራዊት ከሌሊቱ3/00- 6:00 ሰዓት ተጨማሪ 2ካሶኒ መከላከያ ሰራዊት በመጨመር ሻለቃዋን ለማፈንና ወደ ፋኖ ሻለቃዋ ካምኘ ለግባት ያለ የሌለ ሀይሉን ቢጠቀምም ነበልባሎቹ የጀረምስ 2ኛ ሻለቃዎች ፊት ለፊት በመጋፈጥ የተከበረ ቤተ መቅደሳቸውን/ካምፓቸውን/በውሾች ሳያስደፍሩ ቀርተዋል!!
በዚህም በጠላት በኩል 7 መከላከያ እስከወዲያኛው ሲሸኙ በጣም በርካቶች ቁስለኛ ሆነዋል!!

ዘራፊውና ወራሪው የብርሀኑ ጁላ ጦር በደባይ ጥላት ግን ወረዳ ዋና ከተማ ቁይ ላይ እንደ ቀንድ አውጣ ራሱን ቀብሮ ከሚገኝበት በወረዳው እና በመከላከያ ከፍተኛ አመራሮች የገጠር ቀበሌዎችን በመቆጣጠር ግብር ፣አልማ፡ነቀይመስቀል የስፖርተ ወዘተ የሚለውን የተለመደ የዘረፋ ዝባዝንኬ በአርሶ አደሩ ላይ ለመጫን የሞኝ ዕቅድ አቅዶ የተንቀሳቀሰ ቢሆንም ወደ ተግባር ለመቀየር ግን አንድ ኪሎ ሜትር በተንቀሳቀሰ ቁጥር የአስከሬን ክምር እየታቀፈ መመለስ የዘወትር ልማዱ የሆነው በዕለቱም በጀሰምስ 2ኛ ሻለቃ የገጠመው ይሔው ተግባር ነበር!!!

   ይህ በእንዲህ እንዳለ በጀረምረምስ ተለብልቦ የተመለሰው ይህ ወራሪ ኃይል በቀን ጥር 19/2017 ዓ.ም አቅጣጫውኖ በመቀየር ወደ ናብራ አራተኛ ሻለቃ ያቀናው የብርሀኑ ጁላ ድጉማን ጦር በደባይ ጮቄ ብርጌድ ባሉ ሁሉም ሻለቃዎች ቅንጅት በመፍጠር ከመቀመጫው ቁይ ከተማ 2ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው የባባት ቀበሌ ልዩ ስሚ ንፋሳም ተብሎ ከሚጠራው ቦታ ላይ የሙሉ ቀን አውደ ውጊያ ሲካሔድ ከጧቱ 4:00_ሌሊቱ 4:00 ውጊያው የቀጠለ ሲሆን ጠላት በነበልባሎቾ የደባይ ጮቄ ብርጌድ ፋኖዎች ተገርፎ ወደመጣበት ቁይ ከተማ ፈርጦ ገብቷል::

በጠላት ላይም  13ሙትና በጣም በርካታ ቁስለኛ በማድረግ ኪሳራ ያደረሱ ሲሆን ጠላትም የተረፈውን ሀይል እንዲሁም አስከሬኑንና ቁስለኛውን ታቅፎ የሀፍረት ካባውን ተከናንቦ ተመልሶ ፈርጥጧል!!!!በዚህ በዘመቻ ዮሀንስን_አለማየሁን በተሰየመው አውደ ውጊያ ከደባይ ጮቄ ብርጌድ ሁሉም ሻለቃዎች   የተለመደ የውጊያ ቅንጅት በማድረግ ተሳትፈዋል!!!

ከአይን እማኞች እንዳረጋገጥነው የብልፅግናው ዙፋን አስጨባቂ ወታደር ወደ ፋኖ ቀጠና ሲገቡ የመዋጋት ሞራላቸውና ወኔያቸው የላሸቀ በሠሆኑ በከዘራና በዱላ እየተቀጠቀጡ እኖደሚገቡ ተረጋግጧል።

   ታዲያ ይህንን የፋኖን መብረቃዊ ምት መቋቋም ያቃተው ዘራፊ ቡድን የአፃፋ በትሩን በንፁሀን ሀብት ንብረት በማውደም ሔዷል!!!ይህም ልጅህ ፋኖ ነው በሚል በጀረምስ ቀበሌ #የአቶ_ሳሳሁ_አየለን ቤት እህሉን በመዝረፍ የቤት ዕቃውን በማውደም ፍፁም አረመኔያዊነቱን አሳይቷል።

   #ዘመቻ_ዮሀንስ_አለማየሁ የአማራ ተጋድሎ ይቀጥላል!!!
  
   ፋኖ መ/ር ኃ/ማርያም ክበር
የደባይ ጮቄ ብርጌድ ቃል አቀባይ

Ethio 251 Media

28 Jan, 15:36


የማይቀርበት ቀጠሮ!

በዋሽንግተን ዲሲ የሻማ ማብራት ሥነ ሥርዓት!

Ethio 251 Media

28 Jan, 04:12


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር በአርበኛ ፊታውራሪ ወንደሰን ወልደፃዲቅ የሚመራው መቅደላ ብርጌድ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ድል ተቀዳጀ።

በትላንትናው ዕለት ማለትም ጥር 19/2017ዓ .ም የወራሪው የብልፅግና መራሹ የአብይ አህመድ የግል ወታደር ጠዋት ከአለምከተማ በመነሳት ወደ ወንጪት ወንዝ አቅጣጫ ሃይሉን ይዞ ይወርድና በወንዙ አካባቢ ላይ ታች ሲል ይውላል።

ታድያ በቅርብ ርቀት ሲከታተሉት የነበሩት የአርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አዳሙ ደም መላሾች የናደው ክፍለ ጦር መቅደላ ብርጌድ አርበኛ ቀኝአዝማች በቀለ ሻለቃ አናብስቶች የጠላትን ሃይል በመጠጋት ከወንጭት ድልድይ ከፍ ብሎ ጦጣ በረት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከምሽቱ 11:00 ሰአት እስከ ምሽት 12:20 በቆየ ተጋድሎ ጠላትን አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት በርካቶችን እስከወዳኛው በመሸኘትና በማቁሰል ከፍተኛ ድል አስመዝግበዋል።
ይህ ውጤታማ ኦፕሬሽን የተመራው በሻለቃ አዛዡ አርበኛ ይከበር የተመራ ነው።

ክብር ለተሰውት ሰማዕታት
ድላችን በተባበረ ክንዳችን

ከአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል

Ethio 251 Media

27 Jan, 17:14


ሰበር ዜና!

ነበልባሎቹ የአማራን ሆድ አደር የብልፅግና ካድሬዎችን የጀርባ ጠባቂ ሚሊሾችን እየነደሏቸው ነው።

የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ በሃምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን ከልክሌ ዋና ጦር አዛዥነት የሚመሩት ቀጫጭኖቹ እንደ አቦ ሸማኔ የሚፈናጠሩት ክንዳቸው እንደ እሳት ውላፈን የሚፋጁት የሺ አለቃ ሶስት ፋኖ ልዩ ኦፕሬሽን ፈፃሚዎች በቀን 18/5/2017 ዓ.ም ወደ አረርቲ ከተማ ዘልቀው በመግባት በአራት አቅጣጫ በከፈቱት የተኩስ እሩምታ የአገዛዙን ሚሊሻ ከምሽጉ ሲያሯሩጡት አምሽተው በሰላም ወጥተዋል።

አገዛዙ እራሱን ጥምር ጦር ብሎ የሚጠራው ግትልትል ሰራዊት በ17/ለ18 አጥቢያ ለሊት ወደ አከላል ቀበሌ ሺ አለቃ አራትን ለመክበብ ተንቀሳቅሶ 11ሰዓት ከንጋቱ ከበባ ለማድረግ ቢሞክርም ክንደ ብርቱው አንድ ፋኖ በፈፀመባቸው የደፈጣ ጥቃት ለከበባ የመጣውን ግብስብስ ሰራዊት ጀግናው ብቻውን እንደከብት እዬነዳ 4 የአብይን ወንበዴ ሠራዊት ገሎ 3 አቁስሎ ሊከብ የመጣውን እሬሳና ቁስለኛ አስጭኖ ወደመጣበት ልኮታል። ታዲያ 1ለ 10ይልሀል እንደዚህ ነው።
በዚህ በነበልባሉ በትር የተደናገጠው የአብይ ወንበዴ ሠራዊት የአንድ አርሶ አደር መጋዘን በላይተር ነዳጅ አርከፍክፎ በገንዘብ ሲተመን በሚሊዬን የሚቆጠር ንብረት አቃጥለው ፈርጠዋል።

በቀን 18/5/2017 ከምሽቱ 3:30 ገደማ እሳቱ ነበልባል ያሠማራቸው አጥቂዎች በተጠቀሰው ሰዓት ማህል አረርቲ ከተማ በመግባት አንድ የአገዛዙን ሚሊሻ እስከወዲያኛው ከከተማዋ ብሎም ከዚህ አለም በቀይ ጥይታቸው ሸኝተውት በሰላም ወደ ነፃ ቀጠናቸው ተመልሰዋል።

ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ነፃነታችንን በክንዳችን!!!
ክብር ስለነፃነት ለተሠው ሰማዕታት።

መረጃው/ የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለ ጦር የነበልባል ብርጌድ ፋኖ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ነው።

 

Ethio 251 Media

27 Jan, 17:01


ሰበር ዜና!

በወሎ ቤተ አምሓራ ቀንደኛው አስተኳሽ ቴዎድሮስ ብርጌድ  እስከወዲያኛው ተሸኘ!

በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ ውስጥ የ027 ቀበሌ ሊቀመንበር የሆነው አቶ ዳውድ ሙህየ የተባለ ቀንደኛ አስተኳሽ እና ባንዳ በዛሬው እለት ማለትም ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ/ም እስከወዲያኛው ተሸኝቷል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ቤተ አምሓራ ምዕራብ ወሎ ኮር አ/ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር ቴዎድሮስ ብርጌድ አስታውቋል::

መከላከያ፣ ሚሊሻ፣ ፓሊስ እና አድማ ብተናን እየመራ ወደ ቴዎድሮስ ብርጌድ ፋኖዎች የጦር ሰፈር ያስጠጋ የነበረውና በተደጋጋሚ ጥቃት እንዲሰነዘር በማድረጉ የተነሳ በጥብቅ ሲፈለግ የነበረው ይህ ባንዳ በዛሬው እለት ጥር 19 ቀን 2017 ዓ.ም በልዩ ኦፕሬሽን ስፔሻሊስቶቹ የመቅደላ ጀግኖች ጥይት ተመትቶ እስከወዲያኛው ተሸኝቷል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! 

"ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን"
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሐራ)
ጥር 19/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

27 Jan, 14:38


             ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ( ቤተ አምሐራ ) ምዕራብ ወሎ ኮር ዳግም ክተት ወረኢሉ ክፍለጦር በአገዛዙ የፖለቲካ አመራር ላይ ድል ተቀዳጀ!
    
በኢ/ር ናትናኤል አክሊሉ (ቢትወደድ) የሚመራው ዳግም ክተት ወርኢሉ ክፍለጦር ጠላትን በተለያየ ስትራቴጂ በፓለቲካ አመራሩ ካድሬ እና በዙፋን ጠባቂው ጥምር ጦር ላይ እርምጃውን አጠናክሮ ቀጥሏል።

  7ለ52 ብርጌድ ሳተናው ሻለቃ በለገሂዳ ወረዳ መሃል ከተማ በመግባት በአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ጥምር ጦር ላይ እርምጃ በመውሰድ በርካታ የአገዛዙ ሰራዊት ተመተዋል ።

የአገዛዙ ጥምር ጦር ከለገሂዳ ወረዳ ወጥቶ ፋኖን አፀዳለሁ ብሎ ወደ ሽክፍ ከተማ እየመጣበት ባለበት ስአት ንስር ሻለቃ ባታ ይዛ ብጠብቀውም ወደ ሽክፍ ሳይገባ ወደኋላ ሲፈረጥጥ ሳተናው ሻለቃ ለቆት ወደመጣው ወይናአምባ  የወረዳው ከተማ በመግባት የአገዛዙን ጥምር ጦር  እርምጃ ተወስዷል፤ በዚህም ሆዳም ካድሬ ሚኒ ካቢኔ አባል እንደተወገደ መረጃ ለክፍለጦሩ መረጃ ክፍል የደረሰ ሲሆን ማንነቱን አጣርተን ይፋ የምናደረግ ይሆናል።

በሌላ ዜና የወረኢሉ ከተማ ምክትል ከንቲባ ከተሾመ በአራት ቀኑ በኦፕሬሽን መያዙን የክፍለጦሩ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ መ/ር አለባቸው ቀስቅሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

እረገጤ ኪዳኔ የተባለው ከአንድ አመት በፊት የወረኢሉ ዋና ከንቲባ በመሆን ያገለገለ ከዚያም በኢንቨስትመንት ቢሮ ቡድን መሪ እና የማኔጂመንት አባል አማራን በአገዛዙ ጥምር ጦር ሲያስገድል ሲያዘረፍ ህዝብ ሲዘረፍ ቆይቶ ድጋሜ ከተያዘ አራት ቀን በፊት ለሹመት ሲጠየቅ ሌላው አልፈልግም የወደቀ አገዛዝ ሲል እሱ የተቀበለ  ፋኖ ምንም አያመጣም ያለ የአማራ ባንዳ ሲሆን በታየ ተሰማ ሻለቃ ኦፕሬሽን ቲም ተይዟል።

ቀንደኛው ባንዳ ሲያዝ የስራ ላፕቶፕ እና የእጂ ስልክ የተያዘ ሲሆን በረካታ ሰነዶች ተገኝተዋል እጂግ በጣም የሚያሳዝነው ከተገኝው ሰነዶች ውስጥ አንዱ የ666 እምነት የብልፅግና አመራር የሚመዘገቡበት ፎርም ነው ይህን በቴሌግራም የሚላላኩት የኢትዮጵያን እሴት ወግ ባህል እምነት የማያውቀው የሰይጣኑ አብይ  በሚሰጣቸው አቅጣጫ ሲሆን ቡድናች ስውር አጀንዳ ከፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን አለያይተው
ከሆነብን በላይ የሚሆንብን እንደሚብስ ተገንዘበናል፤ ከካድሬው አንደበት የሰራውን ግፍ በቀረፃ የምናደረስ ይሆናል ሲል የክፍለጦሩ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ መ/ር አለባቸው ቀስቅሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

Ethio 251 Media

27 Jan, 12:27


የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎች በጠላት ላይ ድልን ተቀዳጁ!
==============================================

ራሱን መከላከያ እያለ የሚጠራው የፋሽስታዊው አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ የሽብር ቡድን ደብረ ኤልያስ ከተማ ገብቶ በጀግኖቹ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች መገረፍ ከጀመረ ድፍን ሁለት ወራት አልፈዋል።በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ በርካታ የወራሪው ጦር እስከ ወዲያኛው ተሸኝቷል።በርካቶችም ቆስለዋል።
ቀደም ብሎ ካስገባው የጠላት ኃይል በተጨማሪ ከሰሞኑ በርካታ ሰራዊት ማስገባቱ ይታወቃል።ይህም የወረዳውን ገጠራማ አካባቢ ለመቆጣጠርና በዋናነት ግን የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ስላሴ አንድነት ገዳምን በድጋሚ ለማውደም እየተደረገ ያለ እንቅስቃሴ ነው።

ዛሬም ከደብረ ኤልያስ ከተማ ሙሉ ጦሩንና መሳርያዎቹን ጭኖ ወደ ጓይ መገንጠያ በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ ጀግኖቹ የቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎች ከፍተኛ የሆነ ውጊያን በመክፈት ታላቅ ኪሳራን አድርሰውበታል።በአርበኛ ድረስ አለማየሁና አርበኛ ነጋ መኮንን የተመራው ይህ ውጊያ የጠላትን ቅስም የሰበረ ነበር።ጠላት በዙ-23ና በሞርተር የታገዘ ውጊያ ቢያደርግም ቀስተኞቹ ግን ከምሽጋቸው ፍንክች ሊሉ አልቻሉም።

በዚህ ውጊያ በወገን በኩል ቀላል ቁስለኛ ከሆኑ ጥቂት ፋኖዎቻችን ውጭ የተከፈለ መስዋዕትነት የሌለ ሲሆን በጠላት በኩል ግን 16 አምቡላንስና ፓትሮል በቁጠር ደረጃ ከ112 በላይ ቁስለኛ የተነሳ ሲሆን የሟቹን መጠን ግን በተረጋገጠ መረጃ ማወቅ አልተቻለም።ምክንያቱም በየቦታውና ምሽግ ባደረጉት የሳሰር ቤተ ክርስቲያን ይቀብሩት ስለነበር ነው።ይሁን እንጅ ከቁስለኛው በላይ ሊሆን እንደሚችል ግን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸውልናል።

ጠላት በአሁኑ ሰዓት በጎፍጭማ ታዳጊ ከተማና የቀጋት ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚገኝ ሲሆን የትኩረት አቅጣጫውም የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን በድጋሚ ለማውደም እንደሆነ ይታወቃል።

ደብረ ኤልያስ ግን ጠላትን ውጣ ማስቀረቷን ቀጥላለች ትቀጥላለችም።

ድል ለሕዝባችን!
ክብር ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተሰፋ፣አዲስ አስተሳሰብ!

ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው
የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር
የቀስተደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ

Ethio 251 Media

27 Jan, 09:42


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አምደ ጽዮን ኮር በስሩ ያሉ ክፍለ ጦሮችን በማስተባበር ወደ ሬማ ከተማ በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ የተቀናጀ ጥቃት ፈፀመ!

የ 12 ዓመት ህፃን የገደለብንን አራዊት ሰራዊት፤ በሚገባ በአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ተበቅለናል!

ዛሬ ጥር 18 ቀን 2017ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ጀምሮ እራሱን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ብሎ የሚጠራው የሰው በላው ስብስብ በሁለት አቅጣጫ ወደ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ ሚዳ ወረዳ ሬማ ከተማ በተንቀሳቀሰው የጠላት ሀይል ላይ በአርበኛ መከታው ማሞ የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አምደ ጽዮን ኮር የራንቦ ክፍለ ጦር ሻለቃ 4 እንዲሁም የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ልዩ ዘመቻ እና በአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ስር ያሉ ብርጌዶችን በማስተባበር የተጠናከረ እርምጃ ወስደዋል።

መነሻውን ከመርሀቤቴ አለም ከተማ እና ሚዳ መራኛ ከተማ አድርጎ ወደ ሬማ ከተማ የተንቀሳቀሰው የጠላት ሀይል በአማራ ፋኖ የቁርጥ ቀን ልጆች በሆኑት አናብስቶች ሲገረፍ ፣ ሁለቱ ክፍለ ጦሮች በጥምረት በሚገባ በጠላት ሀይል ላይ የበላይነቱን ተጎናፅፈዋል።

ከመርሀቤቴ አለም ከተማ በተነሳው የሰው በላው ስብስብ ላይ እንደ ተርብ የሚናደፉት የራንቦ ክፍለ ጦር ሻለቃ 4 እና የዕዙ ዘመቻ እንዲሁም በአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ምክትል ዘመቻ መኮንን ፋኖ አዘነ ታምር የተመራው የክፍለ ጦሩ ልዩ ዘመቻ ጦር እና የቀስተ ንህብ ብርጌድ ሻለቃ 1 በዋነኝነት የተሳተፉ ሲሆን፤ ከሚዳ መራኛ ከተማ በተነሳው ወራሪው ሀይል ላይ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አስማረ ዳኜ ብርጌድ ሲፋለሙት አርፍደዋል።

ዛሬ እስከ ቀኑ 10:30 ድረስ በተካሔደው አውደ ውጊያ ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ሲያስተናግድ የአራዊት ሰራዊት ቁስለኛ አባላት ወደ መራኛ እና አለም ከተማ ሆስፒታል ሲያመላልስ ውሏል።

በመጨረሻም የአስማረ ዳኜ ብርጌድ ሻለቃ 1 ጦር የጠላትን ሀይል እግር በእግር በመከታተል በስተ ሰሜን አቅጣጫ መራኛ ከተማ ዘልቀው  በመግባት የጠላትን ወራሪ ሀይል ሲያስጨንቁት አምሽተዋል።

በዝሕ የተበሳጨው የጠላት ሀይል የደንጎሬ ጉራንባ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑትን የአርሶ አደር አቶ መልካው ሸንቁጥ ልጅ የ 12 ዓመት ህፃን አባይነው መልካው የተባለን  ምንም የማያውቅ ንፁሃንን ከጓደኞቹ ጋር በመጫወት ላይ በነበረበት ወቅት በጥይት ተኩሶ በመግደል አማራ ጠልነቱን በሚገባ አሳይቷል።

በመሆኑም ጠላት ህልሙ ቅዠት ሆኖበት ወደ መጣበት አለም ከተማ እና መራኛ ከተማ ተገርፎ  ፈርጥጦ ሲመለስ የወገን ሀይል በዜሮ መስዋዕትነት በጠላት ሀይል ከፍተኛ ድል መቀናጀታቸውን የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ምክትል የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሀላፊ ፋኖ መምህር ወርቃፈስኩ  አባቡ ገልፀዋል።


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አምደ ጵዮን ኮር  የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ 

Ethio 251 Media

27 Jan, 09:39


ደብረ ኤልያስ ታላቅ ውጊያ እየተደረገ ነው!

ጀግኖች የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎች ከጠዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምረው ከጠላት ጋር እየተናነቁ ይገኛሉ።

ቀድም ብሎ ወደ ወረዳው ከገባው የጠላት ኃይል በተጨማሪ በርካታ ቁጥር ያለው የጠላት ሠራዊት ከነ ከባድ መሳርያው ከሰሞኑ ማስገባቱ የሚታወቅ ሲሆን ወደ ተለያዩ የገጠር ቀበሌዎች ለመስፋፋት ታስቦ እንደሆነ ታውቋል።በዋናነት ግን የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን በድጋሚ ለማወደም የታቀደ ኦፐሬሽን እንደሆነ ከውስጥ መረዳት ተችሏል።

ውጊያው ከየጨኔ መድኃኔ ዓለም ጀምሮ በመገንጠያና በአድብር አካባቢ እየተካሄደ ይገኛል።

ከጠዋት 12:00 ሰዓት የጀመረው ውጊያ አሁንም የቀጠለ ሲሆን ጠላት በመጀመሪያው  ያደረገው የማጥቃት ሙከራ በወገን ጦር ብርቱ ክንድ ከመክሸፉም ባሻገር በተቃራኒው ለጊዜው ቁጥሩን በዉል ማወቅ ባይቻልም በርካታ የጠላት ጦር መመታት ተችሏል።

ዝርዝር የውሎ መረጃውን የምንመለስበት ይሆናል።

ድል ለሕዝባችን!
ክብር ለሰማዕቶቻችን!

አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተስፋ፣አዲስ አስተሳሰብ

ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው
የአፋጎ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክ/ጦር የቀስተ ደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ

Ethio 251 Media

25 Jan, 16:56


ሰበር ዜና!

ከትናንትናው ዕለት ጥር 16 ቀን 2017 ዓ.ም. ከቀኑ 11 ሰዓት የጀመረው ውጊያ ዛሬም ውጊያው የቀጠለ ሲሆን ምዕራብ ጎንደር ዞን ቋራ ወረዳ ልዩ ቦታው ዱባባ ላይ በተደረገ ውጊያ ከ80 በላይ ጠላት ተደምስሷል።

የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ግዙፉ ቋራ ኦሜድላ ክፍለጦር እና የበጌምድር ክፍለጦር አካል የሆነው አይሸሽም ብርጌድ ባደረጉት ተጋድሎ ከ80 በላይ ጠላት ሲደመስስ፣ 90 የመከላከያ ሰራዊት አገዛዙን ከድቶ ፋኖን ተቀላቅሏል፣ በመደምሰሱና በማስከዳቱ ከመቶ(100) በላይ ክላሽንኮቭ መሳሪያ መገኘቱን የክፍለጦሩ ዋና አስተባባሪ አርበኛ አሸናፊ አለባቸው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

አገዛዙ የፋኖን ምት መቋቋም ሲያቅተው ሰርሰረዲ ላይ ዙ 23 በመተኮስ የገጠር ከተሞችን አውድሟል፣ ንጹሃንንም ገድሏል ሲሉ የአይን እማኞች ለ251 ሚዲያ ገልጸዋል።

ውጊያው አሁንም እንደቀጠለ ነው፣ ፋኖ የበላይነቱን ይዞ እየተዋጋ ይገኛል፣ ዝርዝር መረጃዎችን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

Ethio 251 Media

25 Jan, 13:45


ሰበር ዜና!

ነዳዬቹ ነበልባሎቹ አጥቦ አይነብሴዎቹን በኬላ ጥበቃ ሳሉ በጥይት ነቀሷቸው።

ወደ ጠላት ቀጠና ሰርገው በመግባት ታላላቅ ጀብድ በመስራት የሚታወቁት ቀጫጭኖቹ በሃምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን ከልክሌ ዋና ጦር አዛዥነት የሚመሩት የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ በአገዛዙ ላይ እንደ አልቂት ተለጥፈው ውዱን የአማራ ህዝብ እደፈለጋቸው የሚያሠቃዩት በኬላ ወደ ከተማዋ የሚገቡትን አለምን አርሰው አለስልሰው ዘርተው በላባቸው አለምን የሚቀልቡ ነጭ ጤፍ አምራቾቹን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ አርሶ አደሮችን ከኬስ ሞባይል ጀምረው ለገበያ የያዙትን ገንዘቡ የሚቀሙት ከ7ዓመት ህፃን አንስቶ እስከናቶች ድረስ በመድፈር አለም አቀፍ ወንጀል የሚሰሩት አጥቦ አይለብሴ ሚኒሻዎች ትናንት ከቀኑ 8:30 አካባቢ ቦሎ ጎርጊስ ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ እደለመዱት ኬላ ዘርግተው ንፁሃንን ሲዘርፉ ወደ ቀበሌው እንደ አውሎ ነፋስ የሚከንፉት ቀጫጭኖቹ የነበልባል ፋኖች በተጠቀሰው ሰዓት በቅፅል ስሙ እሳቱ ተብሎ የሚጠራው ፋኖ በመራው ኦፕሬሽን በብልፅግና ንፍጥ ጠራጊዎች ወንበር ወልዋይ ሚኒሾች ላይ የያዙትን የነፃነታቸውን ማህተብ ማፅኛ የተወለወለ ክላሻቸውን አስተካክለው ቃታቸውን ፈልቀቅ ፈልቀቅ በማድረግ አንድ ሴት ሆና በእናቶቿ በእህቶቿ በወገኖቿ የጨከነች ሚኒሻ ላይ ልቧ ላይ አነጣጥረው አንድ ወንድ ሚኒሻ ላይ ደግሞ አንገቱ ላይ አልመው ያለምኩትን አልስትም በማለት የክላሻቸውን ምላጭ ነበልባሎቹ ክንዳቸው እንደረመጥ እሳት የሚፋጀው እነሳቱ ጣታቸው ያረፈበትን ምላጭ ነካ ነካ ነካ አደረጉት እነ አጥቦ አይለብሴ ሚሊሾች በቆሙበት ከጠላቻቸው ምድር ዘጠፍ ዘጠፍ ብለው ሲወድቁ ግዳጃቸውን በብቃት የተወጡት ፋኖች በሰላም ወደነፃ ቀጠናቸው እየሸለሉ ተመለሱ።

ነበልባሎቹ በዚህ ድል ሆነ ሲሉ የአገዛዙ ሰራዊት ስርዓቱን በመጠዬፍ አንድ 100 አለቃ የሻንበል መሪ የኦሮሚያ ወንድማችን እንዲሁም ሶስት ሌሎች የአገዛዙ ሰራዊቶች ወደ አማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክፍለጦር ነበልባል ብርጌድ በመቀላቀል ድሉን እጥፍ አድርገውት ውለዋል አገዛዙም ከመፍረስ አልፎ ወደመትነን ተቀይሯል ሲል የአማራ ፋኖ በሸዋ ከሰም ክ/ጦር የነበልባል ብርጌድ ፋኖ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ኃላፊ ፋኖ መምህር አጥናፉ አባተ ገልጿል።
  
   

Ethio 251 Media

25 Jan, 11:28


ሰበር ዜና!

በኮሎኔል ድባቤ የሚመራው አሸባሪው የብርሃኑ ጁላ ጦር ከሰከላ ወረዳ ወደ ኮለል፣ ጃቮላ ማርያም እና ከበሳ የተባሉ የገጠር ቀበሌወች ከሌሊቱ 4:00 ተንቀሳቅሶ የነበረ ሲሆን ጃቮላ ማርያም ላይ የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ኛ ክፍለጦር ግዮን ብርጌድ ክንደ ነበልባሎቹ ሀይሌ አድማሱ ሻለቃ ከጥዋቱ 2:00-5:00 ከጠላት ሀይል ጋር የተፋለመች ሲሆን ጠላት ሙት እና ቁስለኛ ሲሆን ደሙን በየመንገዱ እየዘራ እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ ሰከላ ፈርጥጧል።

ጃቮላ ማርያም ላይ ዲሽቃ ተክሎ የነበረ ጠላት በአናብስቶቹ ሀይሌ አድማሱ ሻለቃ እጅ ሊገባ ለጥቂት አምልጧል።

ይህ አሸባሪ ሀይል ከበሳ ላይ አባ መኩሪያ ይታይህ የተባለ የ80 አመት ሽማግሌ እና ታደሰ አደራ የተባለ የሱርባ የሱርባ ቀበሌ ተወላጅ የ60 አመት ሽማግሌ ፋኖ ከመድረሱ በፊት ከቤት አውጥቶ የረሸናቸው ሲሆን አንድ ባጃጅም አቃጥሏል።

ይህ ሰው በላ የሆነ ሀይል በተንቀሳቀሰባቸው ቦታዎች ሁሉ ያገኘውን ንጹሀን ከመጨፍጨፍ ወደኋላ የማይል እጅግ አረመኔ የሆነ ሰባዊነት የማየሰማው ሀይል ነው።

ከበሳ የገባውን የአሸባሪው ሀይል በግዮን ብርጌድ በአናብስቶቹ መብረቁ ሻለቃ እና ግትም ሻለቃ አከርካሪውን ተሰብሮ እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ ሰከላ ፈርጥጧል። በዚህ አውደ ውጊያ መብረቁ ሻለቃ 300 የክላሽ ጥይት መማረክ ችላለች።

ይህ ሀይል ከከበሳ ወደ ሰከላ ሲፈረጥጥ በግዮን ብርጌድ አባግስ ሻለቃ ዘረፈንጅ የተባለ ቦታ ላይ ደፈጣ በመያዝ ጠላትን እንደ እባብ ሲቀጠቅጡት ውለዋል። የዛሬው ውሎ የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ኛ ክፍለ ጦር ግዮን ብርጌድ የ4ቱም ሻለቃወች ድንቅ ብቃት የታየበት ሲሆን በሚገርም መናበብ ጠላትን እየተቀባበሉ ሲወቁት ውለዋል ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ኛ ክፍለጦር የግዮን ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ የቻለ አድማሱ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

Ethio 251 Media

25 Jan, 11:11


ሰበር ዜና!

በ61ኛ ክ/ጦር የ3ኛ ሬጅመንት አዛዥና የላስታ ወረዳ ኮማንድ ፖስት አስተባባሪ በተፈፀመበት ጥቃት ቆስሎ ሆስፒታል መግባቱ ተሰማ!

በሰሜን ምስራቅ ዕዝ 61ኛ ክ/ጦር የ3ኛ ሬጅመንት/ሻለቃ/ አዛዥና የላስታ ወረዳ ኮማንድ ፖስት አስተባባሪ የሆነው ሻለቃ ጫላ ትናንት ምሽት በተፈፀመበት ጥቃት ቆስሎ ሆስፒታል መግባቱን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።

የሻለቃ አዛዡ ቆስሎ ወደ ሆስፒታል ሲወሰድ አራት አጃቢዎቹ መገደላቸውን ነው ጣቢያችን ለማረጋገጥ የቻለው።

ትናንት ጥር 16/2017 ዓ/ም በሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ላሊበላ ከተማ ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ገደማ ጀምሮ በከተማዋ ልዩ ቦታ ገጠርጌ በተባለ ሰፈረ ለግማሽ ሰዓት የቆየ ከባድ ውጊያ ተካሂዷል።

ውጊያው የተካሄደው አማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ላስታ አሳምነው ፅጌ ኮር የልዩ ኦፕሬሽናል መምሪያ ክፍል ውስጥ በሚገኙ ጥቂት አባላትና ሻለቃ ጫላን አጅበው በነበሩ ወታደሮች መካከል ሲሆን፡ የላስታ አናብስቱ ድንቅ የውጊያ ጥበብ ተጠቅመው ሻለቃ አዛዡን አቁስለውና አጃቢዎቹ ላይ የማያዳግም እርምጃ ወስደው መውጣት መቻላቸውን ነው የኮሩ አመራሮች ለመረብ ሚዲያ የገለፁት።

በትናንት ምሽቱ ኦፕሬሽን ክፉኛ ከቆሰለው ሻለቃ አዛዡና ከተገደሉት አራት አጃቢዎቹ በተጨማሪ የሻለቃ አዛዡ መንቀሳቀሻ የነበረች አንዲት ወታደራዊ ፓትሮል ከጥቅም ውጭ መደረጓም ነው የተነገረው።

በ61ኛ ክ/ጦር ስር የ3ኛ ሬጅመንት አዛዡና የላስታ ወረዳ ኮማንድ ፖስት አስተባባሪው ሻለቃ ጫላ በከተማዋ የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ፣ ፋኖን ትደግፋላችሁ፣ ብልፅግና ፓርቲን ትቃወማላችሁ፡ በኦሮሞ የሚዘወር የአገዛዝ ስርዓት እንዳይኖር ትፈልጋላችሁ በሚል ጥርጣሬ አራስ እናቶችን ጨምሮ በርካታ ንፁኋኖችን በማፈን አሰቃቂ ግፍ እየፈፀመባቸው የሚገኝ ፀረ አማራ ወታደራዊ አዛዥ መሆኑንም መረብ ሚዲያ ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ ችሏል።

(ምስል፦ በ61ኛ ክ/ጦር ስር የ3ኛ ሬጅመንት አዛዡና የኮማንድ ፖስቱ አስተባባሪ ሻለቃ ጫላ)

ዘገባው፦ የመረብ ሚዳያ ነው!

Ethio 251 Media

25 Jan, 11:10


ማሳሰቢያ!

በወታደራዊ ስነ ምግባር የታነፀ እና ወጥነት ያለው ድርጅታዊ አሰራርን ለመተግበር ሲባል በድርጅታችን የአማራ ፋኖ በጎጃም የህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ከተመደባችሁ የስራ ሀላፊዎች ውጭ ያላችሁ መካከለኛ አመራሮች እና አባላት ምንም አይነት ማህበራዊ ሚዲያ መጠቀም እንታቆሙ ስንል ለማሳሰብ እንወዳለን።

ይህንን ድርጅታዊ መመሪያ ተላልፎ በተገኘ አመራርም ሆነ አባል ላይ ድርጅታዊ ዕርምጃ የምንወስድ መሆኑን የአማራ ፋኖ በጎጃም ይገልፃል።

አፋጎ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!

Ethio 251 Media

25 Jan, 11:08


የወለጋ ክፍለ ሀገር ፋኖ ዕዝ (ቢዛሞ)

Ethio 251 Media

25 Jan, 11:07


" ደም ላይ የበቀለ ወይራ ! "

የፋሽስቱ አብይ አህመድ አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ የፈፀመውን ወንጀል የሚያሳይ ዶክመንተሪ በቅርብ ቀን

Ethio 251 Media

24 Jan, 14:56


የድል ዜና
በጀግናው ሰማዕት ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ የተሰየመው " ዘመቻ ዮሐንስ" ትልቅ ድል አስመዝግቧል ።

ዛሬ በተደረገ ማጥቃት ዋሸራ እና አካባቢው መሽጎ በነበረው የወራሪው መከላከያ ላይ ድል ተቀዳጅተናል።
በዚህ በ"ዘመቻ ዮሐንስ" በአማራ ፋኖ በጎጃም በሁለተኛ ክፍለጦር የንስር ብርጌድ : መብረቁ ተፈራ ቅርጌድ : አበረ አዳሙ ሻለቃ እና ደጋ ዳሞት ብርጌድ ባደረጉት ጥምር ማጥቃት አንድ ሻለቃ የጠላት ሐይል ተደምስሷል ።

46 ሙት : 27 ከባድ ቁስለኛ የደረሰ ሲሆን በነበረው አውደ ውጊያ የተሳተፉ ብርጌዶች ከወትሮው የተለየ ጥምረት አሳይተዋል ።
በጀግናው ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ የተሰየመው "ዘመቻ ዮሐንስ " ተጠናክሮ ይቀጥላል ።

የምንታገለው ሞተን ህዝባችንን ለማዳን ነው !!
አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
(የአማራ ፋኖ በጎጃም )

Ethio 251 Media

24 Jan, 10:08


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሓራ) ምዕራብ ወሎ ኮር ዳግም ክተት ወረኢሉ ክፍለጦር 7ለ52 ብርጌድ ታየ ተሰማ ሻለቃ የአገዛዙን ጥምር ጦር ነኝ ባይ ኃይሉን ከለገሂዳ ወረዳ ወጥቶ በመኪና ወደ ሴደሬ ሲንቀሳቀስ አባ ያንቱ (ይላላ ተክለሃይማኖት) አካባቢ በደፈጣ ድባቅ ተመቷል።

በዚህ ደፈጣ ከ15 በላይ ሙትና ቁስለኛ ማድረግ መቻሉን የብርጌዱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ መሐመድ ሽፈራው ገልጿል።

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

"ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን"
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሐራ)
ጥር 16/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

23 Jan, 18:13


We the Amhara Fano in Shewa wants to express our grave concerns regarding the ongoing human rights violations perpetrated by the genocidal Prosperity regime in Ethiopia. It has been years since this regime began systematically suppressing and detaining politicians, journalists, and activists who peacefully advocate for the rights of the people of Amhara. This suppression has occurred without due process, as individuals are seized from their workplaces, homes, and other locations, often without a court order, utilizing state security forces and infrastructure.

During these years, countless innocent Amharas have endured suffering in various military camps and concentration facilities, all without facing legal prosecution. Even after being unlawfully arrested, they are subjected to egregious conditions, including a complete lack of medical treatment and inhumane treatment. This illegal governmental repression targets Amharas who have no involvement in political dissent, including members of the House of Representatives and others who have been cruelly victimized. Individuals who represent the people, as well as members of the Amhara regional council, have been abducted in violation of their legal immunity. These victims have appeared in court to testify about the inhumane treatment and severe health issues they have been forced to endure.

The Amhara Fano in Shewa demands that the international community break its silence and unequivocally condemn the egregious treatment of prisoners.

We are very concerned about the arrest of Commander Assegid Mekonen,the former leader of the Amhara Fano Showa Command. Despite the regime's media claiming his surrender, his whereabouts remain hidden, and there has been a disturbing lack of verification regarding his existence. The propaganda disseminated by the regime regularly contradicts itself, indicating a lack of respect for the international community, our people, and its own political integrity.Moreover, the contradictory narratives propagated by the regime serve only to obfuscate the truth. The regime claims to have surrendered Commander Aseged Mekon while simultaneously using him for propaganda purposes. It continues to spread misinformation while attempting to negotiate behind the scenes for the Fano forces to surrender. Such actions demonstrate a blatant disregard for the rights of our people and the integrity of political discourse. We urge the global community to take immediate notice of these violations and demand accountability from those perpetuating these human rights abuses.

Abiy Ahmed's genocidal regime has been increasingly weakened from time to time in the Amhara region, and is unable to withstand the resilience of the Amhara Fano forces. As a result of this across the country, particularly in the capital, Addis Ababa, Oromia, and in limited areas of the Amhara region under his control,the regime bears significant responsibility for the loss of countless lives, senting youths to military baracks without formal training against their consent and forcibly deployed them to combat zones without due process.Moreover, this regime is committing egregious war crimes against its own citizens while simultaneously suppressing press freedoms to prevent the international community from accessing vital information.

The Amhara Fano in Shewa expresses its deep concern regarding the man-made famine occurring in North Wolo lasta ayina bugna and Waghemra ethnic districts of the Amhara region. We urge the international community to recognize the dire and devastating impact this famine is having on our people.Our organization calls on the global community to exert pressure on the government to ensure the effective delivery of humanitarian aid and to take decisive action to save the lives of countless children and mothers in peril. Over 120,000 individuals in these districts are currently suffering from severe hunger and urgently require emergency assistance.

Ethio 251 Media

23 Jan, 18:13


Yet, the Disaster Prevention and Food Security Bureau of the state government is disseminating false information and producing misleading reports to obsure the reality of this crisis.Furthermore, the regime is employing heavy weaponry to destroy farmers' crops, exacerbating the famine and threatening to extend its reach to other parts of the region. The Amhara Fano implores the international community to acknowledge the acts of state terrorism and genocide being perpetrated against our people through the regime's multifaceted ethnic cleansing policies. We call for collaboration in delivering humanitarian aid and addressing these egregious violations of human rights.

Glory to our sacrificed comrades!!!
Victory to the people of Amhara!!!

The Amhara Fano in Shewa

Foreign Affairs Department

Ethio 251 Media

23 Jan, 14:08


የእውነተኛ ወንድማማችነት ዋጋ ከአልማዝ ወይም ከወርቅ የበለጠ ውድ ነው!

ከአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የተሰጠ መግለጫና የአንድነት ጥሪ!

የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር በመመስረቱ የተሰማነን ታላቅ ደስታ ለመግለጽ እንወዳለን፣ እንኳን ደስ አላችሁም እንላለን። አንድነት ባለበት ሁሌም ድል አለ። ምክኒያቱም አንድ ስንሆን ጠንካራ፣ ስንከፋፈል ደግሞ ደካማ ስለምንሆን ነው። ለብቻችን ታግለን የተወሰኑ ድሎችን ልናገኝ እንችል ይሆናል፣ አብረን ከታገልን ግን ሙሉ ድል እናመጣለን፣ የአማራ ህዝብን ከጭቆና ቀንበር ነፃ እናወጣለን።

በመካከላችን ልዩነት አይኖርም ማለት አይደልም። ሁሌም የስልት እና ፍላጎት ልዩነቶች ይኖራሉ። ይህ ደግሞ ተፈጥሯዊ ነው። የድል አድራጊነት ዋናው መገለጫ በልዩነት ውስጥ አንድነት ፈጥሮ መታገል መቻል ነው። የትግል ስልታችንን አጣጥመን፣ ግለሰባዊ ፍላጎቶችን ገትተን አንድነት ማምጣት እና ትግላችንን በጋራ ማካሄድ ለነገ የማይባል ጉዳይ ነው። ከዚህ በላይ እኛ በአማራ ህዝብ ላይ የተጋረጠውን የህልውና አደጋ የመቀልበስ ግብን ያነገብን የህዝብ ልጆች ነን። ከዚህ ከትልቁ ግባችን አንፃር ሲታይ ያሉን ልዩነቶች ከዚህ ግባ የሚባሉ
አይደሉም።

በአንድ ላይ የቆሙ ትንሾች የተከፋፈሉ ብዙዎችን እንደሚያሸንፉ ሁሉ፣ ኃይላችን ያለው ከቁጥራችን መብዛት ሳይሆን በአንድነታችን ላይ ነው። የአማራ ህዝብ በቁጥር ብዙ ሆኖ እያለ እስካሁን ደካማ የሆነው አንድነት ባለመኖሩ ነው። በሀገር ውስጥ ሆነ በውጭ አንድነት የጎደለበትና የተሰባበረበት ምክኒያት ደግሞ የትግሉ ማዕከል የሆንነው እኛ አንድ መሆን ስላልቻልን ነው። በአንድ ስም ፋኖ ተብለን እየተጠራን፣ ለአንድ ዓላማ የአማራ ህዝብን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ እየታገልን አንድ መሆን ግን አልቻልነም። ይባሱን ከራሳችን ጋር ጉልበት ወደ መለካካት እና የእርስ በእርስ ግጭት ውስጥ እየገባን ነው።

ጥያቄው ምርጫችን ላይ ነው። እንደ ወንድማማችነት አብሮ ታግሎ፣ አብሮ ማሸነፍ እና አብሮ መኖር ወይም
አሁን እንደምናደርገው እንደ ሞኝ ተነጣጥሎ እና ተጠላልፎ መጥፋትን የአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ምርጫው አንድ እና አንድ ብቻ ነው። እሱም እንደ ወንድማማችነት አብሮ ታግሎ፣ አብሮ ማሸነፍ እና አብሮ መኖር ነው። ይህን የእኛን ሀሳብ ሌሎች ወንድሞቻችንም ሀሳባቸው እንዲያደርጉት ጥሪ እያቀረብን
ከአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ጋር የአንድነት ውይይት እንዲጀመር ጥያቄ እናቀርባለን። በአባቶቻችን መንገድ
ለአንድነት ተገዥ መሆን ያስፈልጋል። አንድነት ወደ ፊት ተጉዞ መሀል ላይ ለመገናኘት መወሰንን ይጠይቃል። የአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ለእውነተኛ አንድነት ቅድመ ሁኔታ የለለው መሆኑን ለማሳውቅ እንወዳለን።

የጋራ ትግል፣ ለጋር ድል፣
ድል ለፋኖ፣ ድል ለአማራ ህዝብ፣
ራስ አርበኛ ደረጀ በላይ
የአማራ ፋኖ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ዋና አዛዥ

Ethio 251 Media

23 Jan, 13:59


ሰበር ዜና!

ዞብል አምባ ክፍለጦር ራያ ቆቦ ቀዩ ጋሪያ እና መንደፈራ ላይ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሐራ) ምስራቅ አማራ ኮር ሁለት ዞብል አምባ ክፍለጦር 2ኛ ሻለቃ ወደ መንደፈራ እና ቀዩ ጋሪያ ለማጥቃት የመጣን የብልፅግናው ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት የተለመደዉን ክንዳቸዉን ያቀመሱት ሲሆን ከ10 በላይ ሙትና ከ15 በላይ ቁስለኛ ይዞ ወደ ቆቦ ከተማ ፈርጥጧል::

ዞብል አምባ ክፍለጦር ራያ ቆቦ ዞብል የመሸገው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ከቆቦ ከተማ በኩል ምንም አይነት ስንቅም ሆነ ንብረት እንዲሁም የሰው ሃይል መጨመር እንዳይችል አድርገው ከመንደፈራ ጀምሮ እስከ ዞብል ተሮ በር የተቆጣጠሩት ሲሆን በዛሬው ዕለት ጥር 15/2017 ዓ.ም ለማስከፈትና ቀጠናዉን ለመቆጣጠር ማጥቃት ቢያደርግም የጀግኖቹን ክንድ መቋቋም አቅቶት ወደ ቆቦ ከተማ ተመልሷል::

በመሆኑም ዙፋን ጠባቂ ሰራዊቱ በራያ ቆቦ በኩል በጀግኖቹ ዞብል አምባ ክፍለጦር ተደጋጋሚ ጥቃት ተስፋ ቆርጦ በአፋር በኩል ስንቅና ተጨማሪ የሰው ሃይል ለማስገባትና ለመጨመር ተገዶ እስከ አፋር ክልል ፎኪሳ ጦሩን አስፍሮ ይገኛል::

ጠላት በዛሬው ተጋድሎ በርካታ ሙትና ቁስለኛ ያስተናገደ ሲሆን እንደተለመደው ሽንፈት በመከናነቡ ንፁሃንን ኢላማ ያደረገ ተኩስ በመክፈት አንድ ንፁህ በግፍ የረሸነ ሲሆን አንድ መኖሪያ ቤትና ንብረቶችን ሙሉ ለሙሉ አውድሟል::

መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

"ህልዉናችን በተባበረ ክንዳችን"
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሐራ)
ጥር 15/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

23 Jan, 07:30


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር በአርበኛ ፊታውራሪ ወንደሰን ወልደ ፃዲቅ የሚመራው መቅደላ ብርጌድ ለልዩ ኦፕሬሽን የተዘጋጁ የፋኖ ሃይሎች በመርሀቤቴ ወረዳ መቀመጫ ዘልቀው በመግባት የአገዛዙ ሚሊሻወች በመደምሰስ ይዘውት የነበረ መሳሪያ በመማረክ ወደ ቀድሞ ቦታቸው ተመልሰዋል።

<<ምከረው ምከረው ካልሰማ መከራ ይምከረው>>

እንዳለው ያገሬ ሰው የአማራን ህዝብ ከምድረ ገፅ አጠፋለሁ በሚል ድንፋታ የብልፅግናው ስርአት ያለ የሌለ ሃይሉን በህዝባችን ላይ ጦርነት ቢያውጅም ከአማራ ህዝብ አብራክ የወጡት አይደለም በህይወት ኖሮ ተሰውቶም የሚፈሩት አርበኛ ቀኝ አዝማች ይታገሱ አዳሙ ከሰማእትነት በፊት ከሚገባው በላይ ጠፍጥፎ በወኔ እና በጀግንነት የሰራቸው አናብስቶቹ ከተማ ውስጥ ሰርገው በመግባት አንመከርም ባሉ ሚሊሻወች ላይ መብረቃዊ ርምጃ ወስደዋል።

ያኔ አባቶቻችን በኢጣልያን ጦርነት ሲፋለሙ በነበረበት ወቅት አርበኛ ፈለቀ እጅጋየሁ እንድህ ብሎ ነበር፦
ለሆድ ተገዝቶ ባንዳ ቢሰበሰብ
መንገድ ላይ ዘርሩት ሌላውም ይሰብሰብ ብሎ ነበር። ታድያ ታሪክ እራሱን ደገሞና ዛሬም አናብስቶቹ ባንዳን አስተማሪ በሆነ ቅጣት ቀጥተዋቸዋል። በባንዳ ሚሊሻ ላይ ከፍተኛ ክስረት የደረሰበት የስረአቱ እና የአገዛዙ ስልጣን አስጠባቂ ጋሻጃግሬ የባንዳን አስከሬን ሲያይ ከትግሉ ጋር ምንም ግንኙነት የሌላቸውን ሁለት ሲቪሊያ ላይ ጉዳት አደርሷል።


ክበር ለተሰውት ሰማዕታት
ድላችን በተባበረ ክንዳችን

ከአማራ ፋኖ በሸዋ ናደው ክፍለ ጦር የሚዲያና ኮምንኬሽን ክፍል

Ethio 251 Media

22 Jan, 19:25


ከአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ-አምሐራ) የተሰጠ የአንድነት መግለጫ!

"የመርጦ ስምምነት" (Merto Declaration)

Ethio 251 Media

22 Jan, 17:00


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ አንድነት በጎንደር ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ተወርዋሪ ክ/ጦር በዛሬው እለት ጥር 14 ቀን 2017 ባደረገው የደፈጣ ውጊያ ወጂ ከተማ ላይ በስበር ሻለቃ ሻለቃ መሪ በሻለቃ ጌትነት፣ በተሰራው ኦፕሬሽን የአድማ ብተና ምክትል ኣዛዡን ጨምሮ 6 የአድማ ና ሚሊሻ አባላትን እስከወዲያኛው መሸኘት መቻሉንና 3ቱን ከባድና ቀላል ቁስለኛ መሆናቸውን ከአይን እማኞች መረዳት ተችሏል።

ከዚህ ባሻገር ተወርዋሪ ክፍለ ጦሩ ከሰሙኑ ባደረጋቸው አመርቂ ዉጊያወች 7 የሚሊሻ አባላት አገዛዙ ጨፍጫፊ እና ዘራፊ በመረዳትና እናም ማህበረሰቡን ማውጋት ግፍ መሆኑን በመረዳትና በመክዳት ወደ ሰላማዊ ኑሯቸው እንደተመለሱ ተረድተናል፤ ሆኖም "ተንጋሎ ቢተፉ ተመልሶ ከአፉ" እንደሚባለው ታሪካቸውም ከሚበላሽ ቀሪ ሆድ አደር አድማ ብተና አባላትና ሚሊሻወች ስርአቱ የወደቀና የበሰበሰ መሆኑን በመረዳትና ወደኛ መጥተው ይቅርታን በመጠየቅ ቢችሉ ወደፋኖ አደረጃጀቶች በመቀላቀል እና ይሄንን የሚገደል የሚዘረፍ የሚደፈር ጭቁን ህዝብ መከራውን ማላቀቁ ላይ የበኩላቸውን አሻራ ቢጥሉ እና የጥሩ ታሪክ ተዋኒያን እንዲሆኑ ካልሆነም ደግሞ ህዝብን ከመውጋት ወደ ሰላማዊ ኑሯቸው እንዲመለሱ ስል ጥሪየን በኢንጅነር ስመኘው በቀለ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ስም ጥሪየን አስተላልፋለሁ።

በስተመጨረሻም በተለያዩ ክፍለ ሃገራት ለምትገኙ ለታላላቅ እና ግዙፍ የፋኖ እደረጃጀቶች በሙሉ የታላቁ ጎንደር አንድነት ሲያሳስባችሁ እና ስትጨነቀልን ለነበራችሁ አርበኞች ከከፍተኛ አመራሮች እስከ ታችኛው የፋኖ አባላት ድረስ ደስ ብሎናል እንኳን ደስ ያላችሁ ደስታችን ወደር የለውም እናም የደስታችን ተካፋይ ስለሆናችሁ እንደ ኢንጅነር ስመኘው በቀለ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው።

የኢ/ስመኘው በቀለ ተወርዋሪ ክ/ጥር
ም/ህ/ግ/ሃ ፋኖ ፍቃዴ አምባው

Ethio 251 Media

22 Jan, 16:59


ጥር 14/2017ዓም

የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ በላይ ዘለቀ ክ/ጦር ዛንበራ ብርጌድ  የሰረው ገድል!!

በዛሬው ዕለት ጥር 14/2017ዓም በደጀን ወረዳ ጉቢያ ከተማ በተደረገው ውጊያ ከ14 በላይ አድማ ብተና የተደመሰሰ ሲሆን በረካታ የአድማ ብተና ሀይል ቁስለኛ ሆነው ከጉቢያ ጤና ጣቢያ በአምቡላንስ ወደ ደጀን ከተማ መሄዳቸው ተረጋግጥል።

ዛንበራ ብርጌድ በጉብያ ከተማ ባአካሄደው ውጊያ ፋኖ አለሙ ያለው የተባለ ጀግና ቆስሎ በጣላቶቻችን እጅ ስጥ ቢባልም ጀግናው እጄን ለጠላት አልስጥም በማለት ስድስት የአገዛዙ ቅጥረኛ አድማ ብተና ሀይል እስከወዳኜው በመሸኜት በጀግንነት ተሰውቷል።

ዛንበራ ብርጌድ ባአካሄደው አውደ ውጊያ የተለበለበው የአገዛዙ ቅጥረኛ፣ዘራፌው፣ወራሪ ሀይል የጤፍ ለማንሳት ወደ ስራ እየሄደች የነበረች ሴት በአሰቃቂ ሁኔታ እረሽኖታል።

Ethio 251 Media

13 Jan, 18:43


ሰበር ዜና

በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ሃውጃኖ ክፍለጦር ራያ አላማጣ ዋጃ ከተማ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

የአማራ ፋኖ በወሎ ምስራቅ አማራ ኮር1 ሃውጃኖ ክፍለጦር ራያ አላማጣ ዋጃ ከተማ ትናትና ጥር 4/2017 ዓ.ም ሌሊት 6:45 ሰብረው በመግባት ዙፋን ጠባቂ ሰራዊቱ ላይ ከባድ ዉጊያ በመክፈት በርካታ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

እኩለ ሌሊት ተጀምሮ ንጋት ላይ በተጠናቀቀው ከባድ ዉጊያ ሪፐብሊካን ጋርድ እየተባለ የሚጠራው የአብይ አህመድ ቅልብ ጦር ዋጃ ከተማ ት/ቤት በተኛበት በተከፈተበት ከባድ ዉጊያ ከ20 በላይ ሙትና ከ11በላይ የቆሰለ ሲሆን ቀሪው ምሽቱን ወደ ራያ አላማጣ ጥሙጋ ከተማ ሽሽቶ አድሯል::

በፋኖ ካሳ አበበ የሚመራው ሃውጃኖ ክፍለጦር አዳሩን ታላቅ ተጋድሎ ያደረጉ ሲሆን ወደ ጥሙጋ የሸሸው ጠላት ንጋት ላይ ዙ23 በመጠቀም ወደ ዋጃ ከተማ ህዝብ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ በመፈፀም በሰው ህይወት በእንስሳትና በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል::

በቀጣይም መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
ወሎ ቤተ - አምሐራ
ጥር 5/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

13 Jan, 14:48


ከነፍጠኞቹ አንደበት ከአርበኛ ይርሳው ደምስ ጋር የተደረገ ቆይታ /
“ዳር ሆነው የሚቀልዱ ፋኖዎች አሉ” /“ፋኖን የመከፋፈል አዲስ እቅድ ይዘው ገብተዋል”

https://youtu.be/C4gyTLe_yWA?si=UbZFzCJ3RK-SDHLy

Ethio 251 Media

13 Jan, 14:13


ሰበር ዜና!

ሃውጃኖ ክፍለጦር ራያ አላማጣ ዋጃ ከተማ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

የአማራ ፋኖ በወሎ ምስራቅ አማራ ኮር1 ሃውጃኖ ክፍለጦር ራያ አላማጣ ዋጃ ከተማ ትናትና ጥር 4/2017 ዓ.ም ሌሊት 6:45 ሰብረው በመግባት ዙፋን ጠባቂ ሰራዊቱ ላይ ከባድ ዉጊያ በመክፈት በርካታ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

እኩለ ሌሊት ተጀምሮ ንጋት ላይ በተጠናቀቀው ከባድ ዉጊያ ሪፐብሊካን ጋርድ እየተባለ የሚጠራው የአብይ አህመድ ቅልብ ጦር ዋጃ ከተማ ት/ቤት በተኛበት በተከፈተበት ከባድ ዉጊያ ከ20 በላይ ሙትና ከ11በላይ የቆሰለ ሲሆን ቀሪው ምሽቱን ወደ ራያ አላማጣ ጥሙጋ ከተማ ሽሽቶ አድሯል::

በፋኖ ካሳ አበበ የሚመራው ሃውጃኖ ክፍለጦር አዳሩን ታላቅ ተጋድሎ ያደረጉ ሲሆን ወደ ጥሙጋ የሸሸው ጠላት ንጋት ላይ ዙ23 በመጠቀም ወደ ዋጃ ከተማ ህዝብ ያነጣጠረ ጭፍጨፋ በመፈፀም በሰው ህይወት በእንስሳትና በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል::

በቀጣይም መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
ወሎ ቤተ - አምሐራ
ጥር 5/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

13 Jan, 12:49


የ8ኛ/በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አውደ ውጊያዎች መረጃ!

የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ/በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ሶማ ብርጌድ ጥር 05/2017ዓም በእናርጅ እናውጋ ወረዳ ፈለገብርሀን ከተማን ለመቆጣጠር ከጥዋቱ 12:00 ሰሀት ውጊያ ሲያካሂድ ውሏል። በፈለገ ብርሀን በተደረገው ውጊያ 9(ዘጠኝ)የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሀይል እስከወዳኜው ሲሸኙ 6(ስድስቱ) መቁሰላቸው ተረጋግጦል።

በፈለገ ብርሀን በነበርው ውጊያ የጠላት ሀይል ከግንደወይን ከተማ ወደ ፈለገብርሀን ከተማ ለድጋፍ በጉዞ ላይ እያለ በ9ኛ/ሳሙኤል አወቀ ክፍለ ጦር አረንዛው ጎንቻ ብርጌድ እና 8ኛ/በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ሶማ ብርጌድ በእናረጅ እናውጋ ወረዳ ወፊት ቀበሌ ላይ ውጊያ አካሂደዋል። በዚህ ውጊያ 7(ሰባት) የጠላት ሀይል እስከወዳኜው ሲሸኑ 3(ስወስቱ)ቁስለኛ መሆናቸው ተረጋግጦል። የአገዛዙ ዘራፌ ሀይል በፈለገ ብርሀን ከተማ ኖሪ የነበርች የልጅ እናት ለፋኖ መረጃ ትሰጫለሽ በማለት በተኮሱት ጥይት ቁስለኛ ሆና ደብርወረቅ የመጀመረያ ደረጃ ሆሲፒታል ህክምና እያገኜች ባለችበት ሰዓት ህይወቶ ማረፏ ተረጋግጧል።

በ8ኛ/በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ስር የሚገኜው ሽፈረው ገርበው ብርጌድ ጥር 04/2017ዓም በሸበል በረንታ ወረዳ ወረጎ ቀበሌ የጡች ጎጥና ገብሲት ቀበሌ ላይ ከባድ ውጊያ አካሂደዋል። ሽፈራው ገርበው በሁለቱ ቀበሌዎች ባካሄደው ውጊያ 1(አንድ) የሚኒሻ አባል እና ከ10(ከአስር) በላይ የአገዛዙ ቅጥርኛ ሰራዊት እስከወዳኛው መሸኙቱን የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ተኛ በላይ ዘለቀ ክፍለጦር ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ይበልጣል ጌቴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

13 Jan, 10:11


ሰበር ዜና!

መቅደላ እና ተንታ ወረዳዎች ድንበር አቅራቢያ የአማራ ፋኖ በወሎ ድል ተጎናፅፏል።

ለምስር ወጥ ብለው ህዝባቸውን በመጨፍጨፍ ስራ ላይ ተሰማርተው የከረሙ ሚሊሻዎች ላይ እርምጃ ተወስዷል::

በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ እና ተንታ ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሰው ቴዎድሮስ ሻለቃ በትናንትናው ዕለት መቅደላ ወረዳ 08 ቀበሌ ውስጥ ፀረ ባንዳ ዘመቻ ከፍቶ ሚሊሻዎችን አይቀጡ ቅጣት የቀጣ ሲሆን በዚህ ፀረ ባንዳ ዘመቻ 3 የሚሆኑት ሚሊሻዎች በአልሞ ተኳሽ ጀግኖች ተመትተው ከመካከላቸው አቶ ገዛኸኝ የተባለው ሚሊሻ ወዲያው ተደምስሶ በዛሬው እለት የቀብር ስነስርአቱ እየተፈፀመ ሲሆን ሌሎች 2 ግብረአበሮቹ ደግሞ ክፉኛ ቆስለዋል::

ከእነዚህ በተጨማሪ ቁስለኛ እና ሟች ሊኖር እንደሚችል ቢገመትም ለማረጋገጥ ስላልተቻለ ይሄነው ብሎ ለመናገር ቢከብድም ሚሊሻዎች ያላሰቡትን ኪሳራ ሲያስተናግዱ ከወገን ኃይል በኩል ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱን የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል አስታውቋል:: ከትናንቱ ውርጅብኝ በሙልጭልጭ የተረፉ የጥምር ጦሩ አባላት በሰላም እጃቸውን ለቴዎድሮስ ብርጌድ ሰጥተው ህይወታችሁን ያትርፉ ሲልም ክፍለ ጦሩ ጥሪ አቅርቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌለኛው የክፍለ ጦሩ ክንፍ የሆነው የሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ አርብ ዕለት በመቅደላ ወረዳ ውስጥ የምትገኘውን ደብረዘይት ከተማን አመሻሽ ላይ መቆጣጠሩን መግለጻችን ይታወሳል፤ የደብረዘይቱን ኦፕሬሽን ውጤት በተመለከተ ዝርዝር መረጃ እንደምናቀርብ በገባነው ቃል መሰረት የሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ በርከት ያለ የነፍስ ወከፍ ትጥቅ መማረኩንና ቁጥሩ በውል ያልተገለፀ ጠላትን እስከወዲያኛው መሸኘቱን ለማወቅ ችለናል።

በጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱንም የአማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ዛሬ ይፋ አድርጓል።

የደብረዘይቱ ኦፕሬሽን በብርጌዱ አዛዥ ፋኖ በለጠ ምትክ (ድሮን) እና በክፍለ ጦሩ ምክትል አዛዥ ፋኖ ሙሀመድ አሊ (ጭንቅየለሽ) የተመራ ስለመሆኑም ነው የክፍለ ጦሩ ህዝብ ግንኙነት ክፍል የገለፀው።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዞኑ ምዕራባዊ ቀጠና ተንታ እና መቅደላ ወረዳዎች አዋሳኝ የሚንቀሳቀሰው ቴዎድሮስ ሻለቃ ወደ ብርጌድ ማደጉ ይፋ ሆኗል::

የሰው ኃይል እና የመሳሪያ አቅሙ ተገምግሞ የሻለቃው ደረጃ መሻሻሉንና ቴዎድሮስ ብርጌድ ተብሎ መሰየሙን ዛሬ ታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓ/ም የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ክፍል አውጇል::

በዚህም መሰረት ከዛሬ ጀምሮ የሚዲያ ባለሙያዎች የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር ቴዎድሮስ ብርጌድ የሚለውን ስያሜ እንድጠቀሙ እናሳስባለን::


ድል ለአማራ ፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
ወሎ ቤተ - አምሓራ
ጥር 5/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

11 Jan, 21:46


የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች አስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍ ማሰባሰቢያ የዙም መርሀ ግብር

https://x.com/mulugetaanberbr/status/1878195873370284069?s=46

Ethio 251 Media

11 Jan, 20:30


ዛሬም በድጋሚ....


ሠላም ለሁላችሁ ይሁን በያላችሁበት።

የፋኖ መሪዋች መልዕክ የሚያስተላልፍበት የገቢ ማሰባሰቢያ ኘሮግራም ጥሪ ለተቋማት, ለአማራ ማህበራት, ለሀይማኖት አባቶች, ለሚዲያዎች, ለማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎች እንዲሁም የአማራ ህዝብ ጉዳይ ይመለከተናል ለምትሉ ተቆርቋሪ ግለሰቦች :-

የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች ለሰብአዊ አገልግሎት ድጋፍ ለማሰባሰብ በዙም ተገኝታችሁ የበኩላችሁን እንድታደርጉ ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን።

ዛሬ Date Saturday January 11 2025
Time 3:00pm - 9:00pm EST

ስርጭቱ የሚተላለፍባቸው መንገዶች
ዙም, በአማራ ጉዳይ የሚሰሩ ዩቲዩቦች, ቲክቶክ, Twitter (X)...ወዘተ

ከትላንትናው ጋር ተመሳሳይ የሆነ ከዚህ በታች ያለውን zoom ሊንክ በመጠቀም ይቀላቀሉን።

ጊዜያዊ የሰብአዊ እርዳታ አሰባሳቢ ኮሚቴ is inviting you to a scheduled Zoom meeting.

Topic: Virtual Fundraising Event
Time: Jan 10, 2025 03:00 PM Eastern Time (US and Canada)
Every day, 365 occurrence(s)
Please download and import the following iCalendar (.ics) files to your calendar system.
Daily: https://us02web.zoom.us/meeting/tZUvdu-grD4rH9Eq23XB-ucXx6bfaqI26sXU/ics?icsToken=DIdJwfis0DIKROUU5AAALAAAAGSxteck4h312OeQEvOnfB8475Q6SBWG1SsyOT_2D94nqhAHOVe-nDP5ocvpSjVUxypnsVgpTCYJGFhgozAwMDAwMQ&meetingMasterEventId=dOCXm5X9TUK5P_cny7TaSA
Join Zoom Meeting
https://us02web.zoom.us/j/81216825155?pwd=rvcajlJdValNusTk7dSwMxQ47bLkQW.1

Meeting ID: 812 1682 5155
Passcode: 507005

---

One tap mobile
+13052241968,,81216825155#,,,,*507005# US
+13092053325,,81216825155#,,,,*507005# US

---

Dial by your location
• +1 305 224 1968 US
• +1 309 205 3325 US
• +1 312 626 6799 US (Chicago)
• +1 646 931 3860 US
• +1 929 205 6099 US (New York)
• +1 301 715 8592 US (Washington DC)
• +1 669 444 9171 US
• +1 669 900 6833 US (San Jose)
• +1 689 278 1000 US
• +1 719 359 4580 US
• +1 253 205 0468 US
• +1 253 215 8782 US (Tacoma)
• +1 346 248 7799 US (Houston)
• +1 360 209 5623 US
• +1 386 347 5053 US
• +1 507 473 4847 US
• +1 564 217 2000 US

Meeting ID: 812 1682 5155
Passcode: 507005

Find your local number: https://us02web.zoom.us/u/kpR4IUSQP

Ethio 251 Media

11 Jan, 18:02


https://www.youtube.com/live/RDiAsHarHvc?si=i4L3hi81rcCKHxK-

Ethio 251 Media

10 Jan, 22:51


https://rumble.com/v67ygej-376161931.html

Ethio 251 Media

10 Jan, 22:50


https://x.com/mulugetaanberbr/status/1877810817774617065?s=46

Ethio 251 Media

09 Jan, 15:58


የአብይ አሕመድ አገዛዝ የአገሪቱ ሪፐብሊክ እንደሚገለፅበት "ፌደራላዊም: ዲሞክራሲያዊም"
መሆን ባልቻለበት የወታደራዊ አገዛዝ ስር ወድቋል።

ወደስልጣን እንደመጣ ጀምሮ የአገሪቱ ችግር መፍቻ መንገድ ወታደራዊ አድርጎ ጦርነት የገዢ ቡድኑ አላማ ማሳኪያ ተደርጓል።

የገዢ ቡድኑ የበላይነት እና የስልጣን ቁጥጥር መሠረቱ ፖለቲካዊ ተቀባይነት እና የሀሳብ የበላይነት ሳይሆን ወታደራዊና የፀጥታ መዋቅር ጥብቀ ቁጥጥር አድርጎታል።

በአጭሩ የስልጣኑን ተቀባይነት ምንጭ በኃይል ለማስፈፀም ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው አይተውት በማያውቁት መንግስታዊ ሽብር እየተጨፈጨፉና በገዢ ቡድኑ የእጅ አዙር ከለላ በሚጠበቅ ኢ-መደበኛ ኃይል እገታ፣ ዝርፊያና አፈና እየተፈፀመባቸው ቀጥለዋል።

ገዢ ቡድኑ በአገሪቱ ያደራጃቸው የፀጥታ ተቋማት አገርንና ዜጋን የሚጠብቁ ሳይሆኑ የአገራቱን ሕዝብ እንደጠላት በመቁጠር በብሔር ለይተው የሚጨፈጭፉ፣ የሚያፍኑ፣ የሚያሳድዱ፣ የሚዘርፉ ፣ የሚያሰቃዩ ተደርገዋል።

ይሔ ሁሉ የአብይ ገዢ ቡድን ከሠራው የፀጥታ ተቋማት አደረጃጀትና የቁጥጥር እሳቤ አሉታዊነት የሚነሱ ናቸው።

በዚህ ጽናትና ምርምር ሰነድም የአገሪቱ የፀጥታ ተቋማት አደረጃጀት እና የቁጥጥር ተግባሮች የፈጠሩትን ብልሹና ፀረ-ሕዝብ ተልዕኮ አኳያ እጅግ በጥቂቱ የሚያነሳ ነው። ካሉት ተቋማት መካከልም ለማሳያ ያሕል ብቻ የሥራ ስምሪት ላይ ያሉ የፀጥታ ሰዎችን የስነምግባር እና የመድሎ ተቋማዊ ምልከታ ለመዳሰስ የሚሞክር የምርመራ ዘገባ ነው።

ከአገሪቱ የፀጥታ ተቋማት ስፋት፣ ከተሠራው የአንድ ወገን ቁጥጥር አኳያ እንዲሁም በየተቋማቱ ከሚደረገው ዓይነተ-ብዙ ወንጀሎች አኳያ ባሕርን በጭልፋ የሚባል አይነት ቢሆንም ሁኔታዎችን ለመረዳት የሚያስችል ጥቆማ ለመስጠት የተዘጋጀ ነው።

በዚህ የመረጃ አሰባሰብ ላይ መረጃዎችን በመስጠት ለተባበሩን የውስጥ አርበኞች ቀድመን ማመስገን እንወዳለን።

መልካም ንባብ!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Jan, 12:37


ለመረጃ ቲቪ ቤተሰቦችና ተከታታዮች፣

የቴሌቪዥን ጣቢያው ለኢትዮጵያ ሕዝብ እያቀረበ ያለውን የመረጃ አገልግሎትና በተለይም የአብይ አህመድ አገዛዝ ጦርነት የከፈተበት የዐማራ ሕዝብ እያካሄደ ባለው የወቅቱ የህልውና ትግል የሚዲያውን ድርሻ ለመገምገምና ቀጣዩን ጉዞ ለመቀየስ የፅሞና ጊዜ እንደሚያስፈልግ ስላመንበት ከዛሬ ጥር 1 / 2017 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰኑ ቀናት ከትምህርት ፕሮግራሞች በስተቀር ሌሎች ፕሮግራሞችን እንደማይተላለፉ እያሳወቅን የሕብረተሰባችን ድጋፍ እስካልተለየን ድረስ በአዲስና በተጠናከረ ሁኔታ እንደምንመለስ እናሳውቃለን።

መረጃ ቲቪ

Ethio 251 Media

09 Jan, 09:16


ጥብቅ ሚስጥራዊ መረጃ

የአገዛዙ የታህሳስ 30 ቀጠሮ !

ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን ሚስጥራዊ መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር እንደሚከተለው አቅርቦታል ።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

08 Jan, 15:50


ሰበር ዜና!

64ኛ ክፍለጦር ተደመሰሰ!

በዛሬው ዕለት ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከንጋቱ 11:30 እስከ 9:00 ድረስ በዘለቀ ትንቅንቅ ደቡብ ጎንደር ቀጠና ክምር ድንጋይ ላይ በቀጠናው የሚንቀሳቀሱት ራስ ጉና ብርጌድ ፣ ጄነራል ነጋ ተገኝ ክፍለጦር እና አንበሳው ጋይንት ክፍለጦር በጋራ ባደረጉት ተጋድሎ 303ኛ ኮር 64ኛ ክፍለጦር 500 ሰራዊት ይዞ ቢገባም 50 ሰራዊት ብቻ ይዞ መውጣት እንደቻለና ቀሪው የብልጽግና ሰራዊት ግን ክምር ድንጋይ ላይ ሬሳውን ውሻ እየጎተተው እንደሚገኝ የራስ ጉና ብርጌድ አዛዥ ፋኖ አማኑኤል ሞላ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

በዚህ ውጊያ ራስ ጉና ብርጌድ እቅዱን በማቀድ ከ500 ሰራዊት 50 ብቻ ይዞ ሲወጣ፤ መቶ አለቃን ጨምሮ ተደምስሷል፤ 7 መከላከያ ሰራዊት፣ 2 ፖሊስ፣ ሚኒሻዎች እጅ ሰጥተዋል፤ እስካሁን በተሰበሰበ መረጃ 4 ብሬንና 97 ክላሽንኮቭ መሳሪያ ተማርኳል። ገና የለቀማ ስራ እየሰራን እንገኛለን ሲል ፋኖ አማኑኤል ሞላ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

303ኛ 64ኛ ክፍለጦር በኮ/ል አሰጋ እየተመራ ቢገባም ኮሎኔል አሰጋ የተሸከመው ስናይፕር ጥሎና ሰራዊቱን አሰጨፍጭፎ ፈርጥጧል፤ ይህ ኮሎኔል በዚህ ውጊያ ላይ ኃይል ጨምሩልኝ እያለ ቢውልም ከጋይንት ለመንቀሳቀስ ቢሞክርም አንበሳው ጋይንት ክፍለጦር መንገድ ላይ ዘግቶ ሲፋለመው ሲውል፣ በሻለቃ ሀብታሙ የሚመራው ሻለቃ ጦርም ከደብረታቦር ለመግባት ጋሳይ ላይ ሲፋለመው ውሏል። አገዛዙ መቀናጀት እንዳይችል አድርገን ፋኖዎች ግን በጋራ ቅንጅት 64ኛ ክፍለጦር ከዚህ በፊት በአንድም በሌላም መንገድ ሲዳከም የነበረ ኃይል ነው፤ ዛሬም ቀሪውን የመፈጻጸም ስራ ሰርተናል ሲል የራስ ጉና ብርጌድ ዋና አዛዥ ፋኖ አማኑኤል ሞላ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

08 Jan, 14:30


በወቅታዊ ጉዳይ ከአማራ ፋኖ በጎንደር እና ከአማራ ፋኖጎንደር እዝ የተሰጠ የጋራ መግለጫ!

የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል በሐቅ፣ በፍትሕና በሰብዓዊ ክብርዓለትነት ላይ የታነጸ ብርቱ አብዮት ነው። አብይ አሕመድ መራሹየብልጽግና ሥርዓት በሕዝባችን ላይ የዘር ማጥፋት አዋጅን አውጆ፣ የሃገሪቱን ጦር አዝምቶ ሠላማዊዉን ወገናችንን መጨፍጨፍ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ መላው የአማራ ሕዝብ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ሥነ ልቡናዊ ምስቅልቅል ውስጥ እንዲገባ አድርጓል።

ሥርዓቱ ጸረ አማራነት አስተሳሰቡን ፍጹም ጭካኔበተሞላበት አረመኔያዊ ግብሩ በገሐድ አሳይቷል። ሕዝባችን ከላይ፦ ድሮንና መርዛማ ቦንቦችን የታጠቁ ጀቶች፣ ከታች፦ መድፍ፣ ታንክ፣ ቤኤም፣ ሞርተርና ዲሽቃ በአማራዊ ማንነቱ ብቻ እንደ በረዶ እየወረዱበት ዘሩ ከምድረ ገጽ እንዲጠፋ መንግሥት መር የዘር ማጥፋት ድርጊት እየተፈጸመበትም ይገኛል።

ይህ አረመኔ ሥርዓት በሕዝባችን ላይ እየፈጸመ የሚገኘውን የጦርወንጀል ለማድበስበስና የሥልጣን ፍትወቱን ለማጽናት ምናልባትምሥርዓተ መንግሥቱን ከውድቀት ለመታደግ የሚጓዝባቸው መንገዶችደመ ነፍሳዊ፣ አላዋቂ፣ ሕገ ወጥ፣ መርኅ አልባ፣ ከምንም በላይ ሀገርንየመምራት ሞራል፣ ክህሎትና እውቀት የሌለው ፍጹም አቅመ ቢስ መሆኑን ያረጋግጣል። ብልጽግናን መታደግ የሞተን ሰው ከመቃብር እንደ ማስነሳት ነው፤ ብልጽግናን እንደ መንግሥት ማስቀጠል የጸሐይን መውጫ በምዕራብ እንደመጠበቅ ነው፤ የብልጽግናን የሥነ መንግሥት ውቅር መሠረታዊ እሳቤዎችን ማስቀጠል በአማራሕዝብ ላይ የሚፈጸምን የዘር ማጥፋት ወንጀል እንደ ማስቀጠል ብሎም የጦር ወንጀሉም ተባባሪነት ነው፤ ብልጽግናን በገሐድ ማስቀጠል አይደለም ሥርዓቱ እንዲቀጥል በንግግርና በሀልዮም ጭምር መደገፍ ታሪክ ይቅር የማይለው አማራ እንደሕዝብየሚጠፋበትን ጦርና ጎራዴ እንደማቀበል ነው።

ስለሆነም ሥርዓቱን ከነእኩይ አስተሳሰቡ ለማስወገድ የሚደረገውን የአማራ ሕዝብየኅልውና ትግልን ለማኮላሸትና ለመጎተት የሚታትሩ ከብልጽግናው መዋቅር ሹማምንት እስከ የሃይማኖት አባትነትና የሽምግልና ጭምብል አጥላቂዎች፣ የአማራን ሕዝብ በምጣኔ ሃብት እያደቀቀ ለሚገኝ ሥርዓት በፋይናንስ ደጋፊ ባለሃብቶች እስከ ሳይበሩ ዓለም የተኮለኮሉ እኩይ የሥርዓቱ ሎሌዎች መኖራቸውን በውል እናውቃለን።

የአማራ ፋኖ በጎንደር እና የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ አደረጃጀቶችበሚከተሉት ጊዜ የማይሰጡ ጉዳዮች ዙሪያ ያላቸውን አቋም፣ አቅጣጫና ማስጠንቀቂያዎችንም ጭምር ለሕዝባችንና ለሠራዊታችን ከምንም በላይ ላላዋቂ የሥርዓቱ ዘቦች መግለጽ እንወዳለን። በዚህ መሠረት፦

1ኛ. ሽምግልና ትርጉሙ፣ አፈጻጸሙ፣ ተሳታፊዎቹ፣ ተጠቃሚዎቹና መሰል ዝርዝር ጉዳዮችን በወጉ ስንመረምር ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ሐቀኛ የፍትሕ ተቋም ነው። እንዲህ ያለ ሐቀኛ ተቋም ደግሞ መርሁፍትሕን በሐቅ ምርኩዝነት መዳኘት ዘወትራዊ ግብሩ ነው። በሽምግልና በዳይን ይገስጹበታል፤ ነውረኛን ያርሙበታል፤ ገዳይን ይቀጡበታል፤ ሸረኛን ቀጥቅጠው ያስተካክሉበታል፤ ሐገርን ሕዝብን ግለሰብንም ጭምር የበደሉ አካላት ያለአንዳች ማኅበራዊ ደረጃ እኩል በሐቅ ይበየንባቸዋል። የተበደሉ አካላትም ይካሳሉ፤ ፍትሕን በልኩ ያገኛሉ። ቅሉ የሽምግልና ወጉ ይህ ሆኖ እያለ ሐቀኛውን ነባር የፍትሕ ተቋም ለሆድ፣ ለጥቅም ማዋል፣ በዳይም ተበዳይም በዓለም አደባባይ እየታወቀ የአይሁድ ሸንጎ አስፈጻሚ የሃይማኖት አባትነትን ጭምብል ያጠለቃችሁ፣ የፍትሕን ምንነት የማታውቁ ነገር ግን በቁሳዊ ሃብታችሁ የታወቃችሁና በልዩ ልዩ ጉዳዮች እውቅናን ያገኛችሁ አካላት በቅንጅት የጦር ወንጀለኛውን በርባን አብይ አሕመድን ነጻ እንዲሆን ሽታችሁ እንደ ክርስቶስ ያለበደሉ መስቀል ላይ የተቸነከረውን አማራውን የማስጨረስ ፕሮጀክቱ ተባባሪ ሆናችሁበማግኘታችን እጅጉን አፍረንባችኋል፤ አዝነንባችኋልም።

በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ የሚገኘው መንግሥት መር የዘር ማጥፋት ድርጊት ከሽምግልና የተሻገረ፣ ሥርዓታዊ ሥር ነቀል ለውጥን የሚሻ፣ ወንጀለኞችም በዓለም አቀፍ የጦር ወንጀልና በዘር ማጥፋት ወንጀል የሚጠየቁበት ጊዜ ሩቅ ስላልሆነ ከወንጀለኛ ጋር የዘረጋችሁትን ተባባሪነት እግራችሁንም እምሯችሁንም እንድትሰበስቡ እየመከርን በየቀኑ የሚገደለው ሰው መሆኑንም ተገንዝባችሁ ለእውነትና ለፍትሕ ያላችሁን ውግንና ጨፍጫፊውን ሥርዓት በአደባባይ በማውገዝ እንድታሳዩንም እንጠይቃለን።

2ኛ. የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል በሥርዓቱ ወራሪ ሠራዊት ላይየውጊያ የበላይነትን ሙሉ ለሙሉ ከመውሰዱ ባሻገር ምድር ላይ ያሉሐቀኛ ሁነቶችን በመግለጥ የሚዲያና የፕሮፓጋንዳ የበላይነት ተወስዶበት መንፈራገጥ ላይ ይገኛል። የተወሰደበትን የሚዲያ የበላይነት ለማካካስ በሚመስል መልኩ በተለያዩ ቀናት የተነገሩትንየድምጽ ቅጅዎች በማገጣጠም የኅልውና ታጋዩን መስተጋብር አበላሻለሁ የሚለው አስተሳሰብና ድርጊትም የሥርዓቱን አላዋቂነት ከመግለጡ ውጭ ከቶ ምንም ሊባል አይችልም። እንደዚህ ያለው የሳይበሩ ዓለም ተግባርም ቀድመን ያወቅነው፣ ድሮን፣ ታንክና ሞርተር ያልበገረው ሠራዊታችንም በወጉ የሚገነዘበው የጠላት እቅድና ፍላጎት መሆኑን እያስገነዘብን፣ አንዳንድ አመራሮቻችን ላይ የሚደረጉ ፍረጃዎቸም የዚህ ፕሮጀክታቸው አካል መሆኑን መግለጥ እንወዳለን።

3ኛ. በመጨረሻም የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግል ብዙ ነገራችንን ያጣንበት በአንጻሩ የብልጽግናን መዋቅር በአጭር ጊዜያፈራረስንበት፣ ሕዝባችንን አስተባብረን በአሸናፊነት መንገድእየተጓዝን የምንገኝበት ግዙፍ አብዮት ነው። እንዲህ ያለውን ሕዝባዊ አብዮት የሚጎትት፣ የሚያቀጭጭ፣ የሚያኮላሽ ምድራዊ አደረጃጀትና መዋቅሮችም ፈርሰዋል። ስለዚህ የማይድን ሥርዓት ውስጥ የምትገኙ የሚሊሻ፣ የአድማ ብተና እንዲሁም የመከላከያ ሠራዊት አባላት እስከ ጥር 15/2017 ዓ.ም ድረስ በየቀጠናው ለሚገኘው የፋኖ አደረጃጀት በሠላማዊ መንገድ እጃችሁን እየሰጣችሁ፣ የተሃድሶ ሥልጠናዎችን እየወሰዳችሁ ሥምሪት ተቀብላችሁ ትግላችንን ወደፊት እንድናስፈነጥረው የመጨረሻ ጥሪያችንን እናቀርብላችኋለን።   
 
ኅልውናችን በተባበረ አንድነታችን!!!
አርበኛ ሐብቴ ወልዴ.............የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ ዋና አዛዥ
አርበኛ ባዬ ቀናው................የአማራ ፋኖ በጎንደር ዋና ሰብሳቢ

Ethio 251 Media

08 Jan, 14:21


ዜና ሹመት!

የአማራ ፋኖ በጎጃም ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ለፋኖ ወግደረስ ጤናው እና ለፋኖ ጥጋቡ መኮንን ሁለት ሀላፊዎችን ሰጥቷል።

በዚህም ፋኖ ወግደረስ ጤናው "የቴሌቪዥን ዝግጅት" ክፍል ሀላፊ ሲሆን ፋኖ ጥጋቡ መኮንን ደግሞ "የማህበራዊ ሚዲያ" ሀላፊ ሆነው ተመድበዋል።

አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!

የአማራ ፋኖ በጎጃም ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

Ethio 251 Media

08 Jan, 13:36


የ10(አስሩ) ኤፍዋን የቦንብ ጨዋታዎች በእናርጅ እናውጋ ወረዳ!!

የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ኛ/በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ስር የሚገኜው ሶማ ብርጌድ በእናርጅ እናውጋ ወረዳ ደጃጋምና ቀበሌ ሳፈቅዳ ጎጥ ላይ ታህሳስ 29/2017 ዓም ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ላይ ሰርጎ በመግባት በጣላት ካንፕ ላይ ከባድ ኪሳራ አድርሷል።

ሶማ ብርጌድ ከደብረወርቅ ከተማ በቅርብ እርቀት የምትገጀኜዋ ደጃጋምና ቀበሌ ሰረጎ በመግባት በወሰደው የሽምቅ ውጊያ 5(አምስት) የአገዛዙ ቅጥርኛ የሆነው ሚኒሻ እና ፖሊስ እስከወዳኜው መሸኜታቸው ተረጋግጦል።የሶማ ብርጌድ (Special Force) አባላት ሰረገው ገብተው በወሰዱት እርምጃ ከ4(አራት) በላይ ቀላል እና ከባድ ቁስለኛ ሆነው ደብረወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆሲፒታል መግባታቸው ተረጋግጧል።

በሶማ ብርጌድ ከፍተኛ ኪሳራ ገጥሞት ከሞት አፍፍ የተረፈው የአብይ አህመድ ዘራፌ ሀይል የሆነው ሚኒሻ እና ፖሊስ በእናርጅ እናውጋ ወረዳ አረጊሚት ቀምባታ ቀበሌ በግብርና ስራ የሚተዳደረው አቶ ጥሩሰው አሞኜ ወስደው እረሽነውታል ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም 8ተኛ ክፍለጦር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ ይበልጣል ጌቴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

Ethio 251 Media

07 Jan, 20:37


የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አመራሮች አርበኛ ዘመነ ካሴን ጨምሮ በወቅታዊ ጉዳዮች መልዕክት አስተላልፈዋል!

Ethio 251 Media

07 Jan, 20:34


ዋርካው ምሬ ወዳጆ
የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ በወቅታዊ ጉዳይ መግለጫ ሰጥቷል።

Ethio 251 Media

07 Jan, 17:56


ከአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ዋና ሀላፊ አርበኛ መ\ር ያሬድ ገደፍው የተላለፈ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት!! =============
በአራቱም ክፍለ ሀገራት የምትገኙ የፋኖ መሪዎች፣  አባላት፣ ለአማራ ህዝብ እንዲሁም ውድ ኢትዮጵያዊያን ጨምሮ   ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም እንኳን አደረሳችሁ !! አምላካችን መድሃኒታችን፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ሰማያት ወርዶ፣ ከእመቤታችን ድንግል ማርያም ተወልዶ፣ የአዳምን ልጆች ከጨለማ ወደ ብርሃን፤ከሲኦል ወደ ገነት  የመለሰበት ታላቅ በዓል ነው። ፋኖ  ማምለጥን፣ መሸሽን፣ እጅ አለመስጠትን ከአባቱ የወረሰው የአማራ ፋኖ በአራቱም ክፍለ ሀገራት በጠላት ላይ ዛሬም እንደ ትናንቱ ክንደ ነበልባሉነቱን አጠናክሮ ቀጥሎበታል። ጥበብ ዋጋ ትከፍላለች። በዓሉን ስናከብር ለአማራ ህዝብ ልእልና ለመመለስ እና ከባርነት ቀንበር ነፃ ለማውጣት በዱር በገደሉ ለተሰው  ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን እንደተለመደው በህሊና ፀሎት ማሰብ እንዳለብን ጠቁሟል።

የተከበራችሁ የጉና ክፍለ ጦር  አመራሮች፣የብርጌድ መሪዎች በየደረጃው ያላችሁ አባላት፣አሁን ያለንበት መድረክ የሚጠይቀውን ፅናትና መስዋእትነት በውል ተረድታችሁ ህዝባችን፣ ለማዳን በሚደረገው ሁለንተናዊ ትግል ግንባር ቀደም ድርሻችሁን እንድትወጡ አርአያነታችሁን አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ የጉና ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ጥሪውን ያቀርባል።

ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!

የጉና ክፍለ ጦር የህዝብ ገንኙነት ፋኖ መ/ር ያሬድ ደገፋው!!

Ethio 251 Media

07 Jan, 17:50


"የልደት በዓል በሰላም ተጠናቀቀ!"

የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳመነዉ ኮር በተቆጣጠራቸዉ ሁሉም ቀጠናዎች የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በሰላም ተጠናቅቋል።

በተለይ ደግሞ በዳግማዊት ኢየሩሳሌም የትናንቷ ሮሃ(አዳፋ) የዛሬዋ ቅዱስ ላሊበላ ከተማ እና ዙሪያዉ ላስታ (የዛጔዬ ስርዎ መንግስት ማዕከል) በየአመቱ የሚከበረው የልደት በዓል የላስታ አሳመነዉ ኮር 7ቱ ክፍለጦሮች ፋኖ የአሳመነዉ ሃይል ሰራዊቱ እና ታላቁ የአማራ ህዝብ በጋራ አክብረዋል። ምንም እንኳን አገዛዙ የሃይማኖታዊ በዓሉን ድባብ ለመቀየር ቢሞክርም እኛ ግን ቅዱሱ፣ ካህኑ እና ንጉሱ ላሊበላ ስንል፣ ከየሀገሩና አህጉሩ ለመጡ ምዕመናን ስንል፣ ለቅርሱ ደህንነት ስንል በዓሉ የተከበረበት ከላሊበላ ከተማ 3 ኪ.ሜ ርቀት ሆነን በዓሉን ከማዶ እየታደምን አሳልፈነዋል።

ደጉ አማራዉ ህዝባችን እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ለሰራዊቱ የበዓል ስጦታዎችን ያበረከተ ሲሆን ግዙፉ ኮራችንም በተቻለ መጠን ለሁሉም ክፍለጦሮች የበዓል ድጎማ በማድረግ ለአማራ ህልዉና ነፃ ታጋይ (የገንዘብ ደሞዝ የሌለዉ) ለሆነው ሰራዊቱ በዓሉን በደስታ እንዲያሳልፉ ጥረት ተደርጓል።

በዓሉም በሰላም ተጠናቅቋል። ስለሆነም በዱር በገደሉ ለአሳመነዉነት ርዕዮት፣ ለአማራ ህዝብ ነፃነት፣ ለፍትህና ለእዉነት እየተጋላችሁ ያላችሁ መላዉ የአሳመነዉ ኮር የክፍለጦሮች አባላት እና ሰራዊቱ እንዲሁም ህዝባችን በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ላደረጋችሁት ሁለንተናዊ ሥራ በእጅጉ እናመሰግናለን።

"አሳመነዉነት ርዕዮታችን፣ ፋኖነት ክንዳችን"
ድል ለአማራ ህዝብ
ድል ለፋኖ
ታህሳስ 29/217
የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳመነዉ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል

Ethio 251 Media

07 Jan, 15:15


#ከአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ አምደ ጽዮን ኮር  አፄ ዳዊት ክ/ጦር የፊት አውራሪ አስማረ ዳኜ ብርጌድ   የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን አስመልክተው ያስተላለፉት መልዕክት!!

➙እንኳን ለ2017 ዓ.ም  የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በፅናት አደረሳችሁ!!!

እየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ የተወለደው  ለመሞት እና የሰው ዘርን ለማዳን ነው። ለዚህ  ነው የክርስቶስ ልደት የሚያስደስተን ፣ግን ክርስቶስ ለኛ ብሎ  ለመገረፉ ፣መሰቀሉ ፣መሞቱ  እንደማይቀር አውቀን ደስ ብሎናል። ለዚያም ነው "አይኔ ማዳንህን አይቷልና ባሪያህን አሰናብተው" ያሉ አባቶች።

የአማራ ፋኖም ሲያዩት ትጥቁ ፣አለባብሱ ፣አካሄዱ ፣ንግግሩን ስናይ ደስ ይለናል። የቁርጥ ቀን የአማራ ፋኖ ፣ካልተዋጋ ፣ ድል ካልተጎናፀፈ ፣ ሰማዕት ካልሆነ ነፃነት የለም።

ክርስቶስ ሲወለድ ደስ እንዳለን ሁሉ ፋኖ ሲደራጅም ደስስ ይለናል። የመጀመሪያው ዘላለማዊ ነፃነት የሚሰጠን ሲሆን ሁለተኛው ግን አለማዊ ነፃነትን የሚያቀጃጅ ነው።

ጀግኖች ሰማዕታት ፣ጀግኖች ፋኖዎች ፣የተከበርከው ህዝባችን በድጋሜ እንኳን አደረሳችሁ!!!

የግፉዓን አምላክ ከኛ ጋር ነውና ድልበድል እየሆንን ትግሉን አጧጡፈን እየቀጠልን ነው። ሙሉ የድል ዋንጫን በቅርብ ይዘን የምንመጣ ይሆናል ።

➙የዛሬውን የገና በዓል ስናከብር ለየት የሚያደርገው በቀን 27/2017 ዓ.ም መነሻውን ከመርሀቤቴ አውራጃ ሚዳ መራኛ ያደረገው የጠላት ጥምር ጦር ክንደ ነበልባሎቹን ለማጥቃት ወደ ተጎራ ቀበሌ ያቀና ቢሆንም በህዝብ ልጅ ፋኖ አይቀጡ ቅጣት በቀጣንበት እና ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ የጥላት አከርካሪው የሰበርንበት ማግስት መሆኑን ስናስብ የፊት አውራሪ አስማረ ዳኜ  ብርጌድ ከፍተኛ አመራሮች እና አባላት ደስታችንን አጥፍ ድርብ ያደርገዋል ሲሉ ተናግረዋል።

በድጋሜ መልካም በዓል ይሁንላችሁ እያልን !!


ሸዋ ፣አማራ፣ኢትዮጵያ !
ድል ለአማራ ህዝብ!!
ድል ለአማራ ፋኖ!!

"የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አምደ ጵዮን ኮር  የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል "

  ድል ለፋኖ!!!

       ታህሳስ 29/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

07 Jan, 12:26


የማይቀርበት ቀጠሮ!

Ethio 251 Media

07 Jan, 09:32


ሰበር ዜና!

ወሎ ቤተ-አማራ በቀጠለው የህልውና ተጋድሎ የአማራ ፋኖ በወሎ በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የሚመራው ባለሺርጡ ክፍለጦር 4ኛ ሻለቃ በቦከክሳ ከተማ የሥርአቱ ወንበር ጠባቂና ሆድ አደር ሚሊሻና አድማ ብተና ላይ መብረቃዊ ጥቃት ፈፅሟል፡፡

በተጋድሎውም በማህበረሠቡ ላይ ቤት ለቤት እየገቡ ዘረፋ፡ ድብደባ እንዲሁም ሴት እህቶቻችንን እየደፈሩ መሆኑ መረጃ የደረሰው ነበልባሉ ፋኖ በያዘው ደፍጣ ከነበሩበት ካምፕላይ በ28/04/2017 ከረፋዱ 4:35 በተከፈተባቸው ድንገተኛ ውጊያ; 7ሙትና 5 ቁስለኛ ማድረግ ቸችሏል፡፡

በዚህ አውደ ውጊያ የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት በደረሰበት ጥቃት የነበረበትን ካምፕ ትቶ ሲፈረጥጥ ካምፑ ውስጥ በቂ ተተኳሺ፡የመሣሪያ ካዝና እና የብሬን ሸንሸል ከነተተኳሹ መማረክ ሲቻል ,የዙፋን ጠባቂው ሰራዊት ቁስለኛ መሥጊድ ውስጥ እየገቡ እያየናቸው ,መሣሪያ ይዘን የእምነት ተቋም መግባት ስለማንችል ባሉበት ትተናቸው ወደ ነበርንበት ካምፕ በድል ተመልሰናል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ የባለሺርጡ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ መምህር መሀመድ ሞገስ ለጣቢያችን አሳውቋል።

Ethio 251 Media

06 Jan, 20:19


ከአማራ ፋኖ በጎንደር የተላለፈ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት!

በቅድሚያ በትግል ሜዳ ላይ ያላችሁ አርበኞች፣ በመላው ዓለም የምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለብርሐነ ልደቱ አደረሳችሁ እያልን !!!

የአማራ ሕዝብ ቱባ ሃይማኖታዊ እንዲሁም ባሕላዊ ክብረ በዓላቶቹ፦ የማኅበረሰባዊ ጥብቅ መስተጋብሮች፣ የአንድነት ድሮች፣ የፍቅርና የሠላም ሸማዎች ይልቁንም ለአእምሯዊ ሃሴት መቀንበቢያ ረቂቅ የማኅበረሰብ ድርሳናት ናቸው። በበዓላት ዋዜማ የተጣሉት ታርቀው በአንድነት ይውላሉ፤ በበዓላት እለት የተነፋፈቀ ቤተሰብ በጋራ ተሰብስቦ በፍቅር ያሳልፋል፤ በበዓለት ወቅቶች የተራቡት ይጠግባሉ፤ የታረዙት ይለብሳሉ። እንዲህ ያሉ ሃይማኖታዊና ባህላዊ ትሩፋቶችን በመቁረጥ ላይ የተጠመደ ነባር እሴትና ትውፊትን አጥፊ ሥርዓት እንደቋጥኝ ተጭኖን ሠላምን፣ ማኅበራዊ አንድነትን፣ ፍቅርን፣ ፍትሕንና ነጻነትን ተነፍገን ከምንም በላይ ማንነት ተኮር የሞት አዋጅ እንደሕዝብ ታውጆብን በኅልውና ትግል ላይ እንገኛለን።

ብርሐነ ልደቱ፦ በዲያቢሎስ እኩይ ሴራ በሰማይና በምድር፣ በእግዚአብሔርና በአዳም ልጆች መካከል የነበረን የጥል ግድግዳ ማፍረሻ፣ ደቂቀ አዳም በሙሉ ከክፉ ገዣቸው የባርነት ቀንበር መውጫ ኅያው ትዕምርት ነው። ልክ እንደዚሁ ሁሉ የአማራ ሕዝብ የኅልውና ትግልም ጨካኙን አማራ ጠል አስተሳሰብና ሥርዓት ማስወገጃ፣ ጥልን፣ አድሏዊነትን፣ ጨፍጫፊነትን፣ ሽብርተኝነትን፣ ዘር አጥፊነትን በማስወገድ ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሰው ዘር በሙሉ ሰብዓዊ ክብሩ ተጠብቆለት በሠላም በአንድነት የሚኖርባት ሀገር እንድትኖር የሚደረግ ትግል ነው።

ብርሐነ ልደቱ የፍስሃ ሆኖ እያለ በአማራው ሕዝብ ዘንድ ግን የለቅሶና የሃዘን በዓል ነው፤ ብርሃነ ልደቱ የምስራች ሆኖ እያለ የአማራ እናቶች፣ አረጋውያንና ሕጻናት ግን በድሮን እየተጨፈጨፉ፣ ተፈጥሯዊ በሕይወት የመኖር መብታቸውን ተነጥቀው የሃዘን ማቅ ለብሰው የሚገኙበት ዓመትና ዘመን ነው። በመሆኑም ይህንን የመከራ ቀንበራችንን ሠብረን፣ ነጻነታችንን የምናውጅበት የኅልውና ትግላችንን አጠናክረን በመቀጠል፣ የብልጽግናን የመርገም ጨርቅ አሽቀንጠረን የምንጥልበት የአርበኝነት ተግባራችን ላይ እንድናተኩር በብርቱ እናሳስባለን።

በመጨረሻም መላው የትግል ጓዳችን በበዓላት ምክንያት መዘናጋቶች እንዳይኖሩ እያሳሰብን በድጋሜ እንኳን ለብርሐነ ልደቱ አደረሳችሁ እንላለን።

ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!
አርበኛ ባዬ ቀናው
የአማራ ፋኖ በጎንደር ሰብሳቢ

Ethio 251 Media

06 Jan, 20:08


እንኳን ለልደት (የገና) በዓል በጽናት አደረሳችሁ!

ከአማራ ፋኖ በወሎ የተሰጠ መግለጫ!

በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላው ዓለም ለምትገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በጽናት አደረሳችሁ! አደረሰን!

ጌታቸን ጽንሰቱ ናዝሬት ውልደቱ በዳዊት ከተማ ቤተልሔም እንደሆነ ሁሉ የእኛም ትግል መነሻ ከየአካባቢው መገፋት፣ መገደል፣ በቃኝ ብሎ የተነሳ አደረጃጀት ቢሆንም መዳረሻች ከአባታቶቻችን ከምኒሊክ ከተማ ስለመሆኑ የሰናፍጭ ቅንጣት ታክል አንጠራጥርም፡፡

ኢየሱስ ክርስቶስ በልደቱ በሀጢያት የወደቅነውን ወደ ቀደመ ማዕረጋቸን ሊመልሰን እንደመጣ ሁሉ፤ አማራም መዋቅራዊ ጥቃት ተከፍቶበት ባለፉት አስርተ አመታት ሲፈናቀል፣ ሲገደል ማህበራዊ እረፍት ተነስቶ እንዲወድቅ እንዲጠፋ ሲሰራበት፣ ፋኖም አማራን ወደ ቀደመ ክብሩና ማዕረጉ ለመመለስ እየታገለና በድል ጎዳና በሚገኝበት ወቅት እንኳን በጽናት አደረሳችሁ መልዕክት ሲያስተላልፍ ለሰፊው አማራ ሕዝብ ትግሉን ከዳር ለማድረስ ቃል እንደ መግባት ነው፡፡

በዓሉን ስናከብር እየሱስ ክርስቶስ መወለድንና ታሪኩን እያሰብን ለሰው ልጅ ሁሉ ዝቅ ብሎ መከበርን እንዳስተማረን ሁሉ እኛም የፋኖ ሰራዊቶች ለሕዝባችን አንድ ነፍሳችን ለመስጠት እስከ ወጣን ድረስ ሕዝባችን በአከበረና በሚመጥን መልኩ እንድንቅሳቀስ ማሳወቅ እንወዳለን።

በቀጣይ አመት የአማራ ሕዝብን የህልውና አደጋ ቀልበሰን ህልው አደርገን በደስታና በፍቅር እንድናከብረው ሁላችንም ለዛ እንድንተጋ እንደ አማራ ፋኖ በወሎ ጥሪ እናቀርባለን።

ዋርካው ምሬ ወዳጆ
የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ

Ethio 251 Media

06 Jan, 18:01


ከአማራ ፋኖ በጎጃም ወታደራዊ መምሪያ የተሰጠ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት!

ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው
የአማራ ፋኖ በጎጃም ም/ሰብሳቢና ወታደራዊ አዛዥ!

Ethio 251 Media

06 Jan, 17:59


እንኳን ለጌታችን ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል #በጽናት አደረሳችሁ!

ከአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የተሰጠ መግለጫ!

ለመላው የአማራ ሕዝብ፣ ለመላው የአማራ ፋኖ፣ ለትግላችን ደጋፊዎች ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2017 ዓ.ም የጌታችን የመድሐኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በጽናት አደረሳችሁ።

በእርግጥ በዚህ ሰዓት የአማራን ህዝብ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ ማለት እንደመሳለቅ ስለቆጠርነው በጽናት አደረሳችሁ ማለትን መርጠናል፤ ከድካም በኋላ የሚገኝ እረፍት፣ ከሞት በኋላ ትንሳኤ እንዳለ መረዳት ያስፈልጋል። የአማራ ሕዝብ በአገዛዙ ግልፅ ሴራ እየደረሰበት ያለውን ሁሉን አቀፍ ጥቃት በመቀልበስ የህልውና ትግል ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚወገድ በሙሉ ልብ በመተማመን በዓሉን በታላቅ ተስፋና ብስራት እናከብራለን።

ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በከብቶች በረት የተወለደው ለክብሩ የሚመጥን፣ ኃያልነቱን የሚያሳይበት ሌላ የተሻላ ቦታ አጥቶ ሳይሆን ዝቅ ከፍ እንደሚያደርግ በልቡ እንደተረዳ እሙን ነው። በአማራ የህልውና ትግል ተሳትፎ እያደረገ ያለ ሁሉ ይሄ ትምህርት በአግባቡ በመረዳት ሁሉም ነገር ከህልውና በታች መሆኑን ተረድቶ የአማራ ሕዝብ የገጠመውን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ ዝግ ብሎ እንዲታገልና ለአንድነት እንዲታገል ማስታወስ እንፈልጋለን።

በዛሬው ዕለት የአሸባሪው አገዛዝ ቁንጮ አብይ አህመድ የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ መግለጫ መስጠቱንም ተመልክተናል፤ በመግለጫውም ስለሰላም ሲዘብዝብ ተመልክተናል። የአማራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ በሰላማዊ ሰልፍ "የአማራ ሕዝብ መገደል ይቁም፣ አማራነት ይከበር፣ አዲስ አበባ እንዳንገባ የሚደረገው ክልኸላ ይቁም፣ በቃ... ወ.ዘ.ተ." ስንል "እነዚህ ደግሞ መቼ ነው ከሰላማዊ ሰልፍ የሚወጡት፣ አልቅሱ ሶፍት እንሰጣችኋለን፣ ወዘተ" ሲሉን እንዳልነበር ዛሬ ተገልብጠው የሰላም ሰባኪ ሁነው መጥተዋል። ስለሆነም ከእንደዚል አይነት ሴራ እንዳይወዘገብና የአማራ ሕዝብ በፋኖነት መር የጀመረውን ትግል አጠናክሮ እንዲቀጥል ሁሉም አማራዊ ግዴታውን እንዲወጣ እንገልጻለን።

በዓሉን ስናከብር አገዛዙ በፋኖ ሰራዊትና በሕዝባችን ላይ የድሮን ጥቃቶች ለመፈፀም እንደተዘጋጀ መረጃውን አነፍንፎ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የመረጃና ደህንነት መምሪያ ክፍል ደርሶበታል፤ ስለሆነም ሰራዊታችንም ሆነ ሕዝባችን ከምንጊዜውም በላይ በተጠንቀቅ ላይ በመቆም በአይንጥቅሻ እየተግባባን እንድናከብር ዕዙ ያሳስባል።

በመጨረሻም ይህንን በዓል ስናከብር በአማራነታቸው ብቻ የተገደሉትን፣ የታሰሩትን እነሱንና ቤተሰቦቻቸውን፤ ለአማራነት ሰማዕትነት የተቀበሉ የጀግና ፋኖ ቤተሰቦችን በማሰብና በማገዝ እንድናሳልፋና በአማራነት እሴት እንድናከብር ስንል እንገልጻለን።

ሻለቃ ሀብቴ ወልዴ
የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ

Ethio 251 Media

06 Jan, 17:52


እንኳን ለ2017 ዓ.ም የገና(የልደት) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!!

የአማራ ፋኖ በጎጃም ታህሳስ 28/2017 ዓ.ም

††††††††††††††††††††††††††††††
#የጎጃም አገው ምድር(3ኛ) ክፍለ ጦር አካል የሆኑት የዳንግላው #ቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ብርጌድና የፋግታ ለኮማው #፲ አለቃ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ በጥምረት በስቦ መምታት የውጊያ ስትራቴጂ ወደ #ጊሳ ንዑስ ከተማ ግብቶ የነበረውን የቀንዳውጣና የአብይ አህመድን ጥምር ገዳይ ቡድን ሌሊት በ3 አቅጣጫ በማፈን ሙሉ ኃይሉ ተደምሷል።

በትናንትናው ዕለት የዳንግላ ወረዳ ዋና አስተዳድሪውን ጨምሮ ከ7 በላይ ካድሬዎች ቤተ ክርስቲያን ላይ በመቆም የፋን ስም ሲያጠለሹና እራሳቸንው ቁዱስ አስመስለው ሲለፈልፉ ውለው ማታ ነው በፋኖ ታፍነው የለፈለፈ ምላሳቸውን በጥይት እርሳስ የተቆረጡት።

በአውደ ውጊያው ከጥይት የተረፉት የወረዳውን ዋና አስተዳዳሪ ጨምሮ ከ7 በላይ ካድሬዎች ተማርከዋል።
ከ110 በላይ ክላሸንኮቭ መሳሪያና ቁጥሩ ያልታወቀ ተተኳሽ ተማርኳል።

እንደ ብሬልና ስናይፐር ያሉ የቡድን መሳሪያዎች ቤት ውስጥ ተጠርንፈው ባለበት ሁኔታ ውስጥ የተደረገ ድንገተኛ ኦፕሬሽን ስለነበር ቤት ውስጥ የመሸገው ገዳይ ቡድን መሳሪያዎችን ላለማስወሰድ ባደረገ ብርቱ ትግል ጀግኖቹ የቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ልጆችና የ፲ አለቃ ኤፍሬም ልጆች ቤቱን በቦብን ሲያጋዩት ውስጥ ላይ የነበረው ጠላት ከነቡድን መሳሪያዎቹ ጋይቷል።

#የ5ኛ(ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም) ክፍለ ጦር አካል የሆነው #ወርቅ አባይ ብርጌድ #አርቢት በሚባል ቦታ ላይ ሲዘርፍና ንጹሃንን ሲገድል የነበረውን ገዳይ ቡድን ባደረገው መብረቃዊ ጥቃት በርካታውን ሙትና ቁስለኛ አድርጎ ቀሪው ፈርጥጦ ወደ እሁዲት ከተማ በመግባቱ ለጊዜውም ቢሆን ሕይወቱን አትርፏል።

ይሄ ጠላት በአርቢት ከተማ የግለሰቦችን ከ10 በላይ ማተር ተሽከርካቶሪዎችን አቃጥሏል። የአርሶአደሩን ሰብል አውድሟል።

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!

ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ
የአማራ ፋኖ በጎጃም ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ምክትል ኃላፊ

Ethio 251 Media

06 Jan, 17:41


የአገዛዙን እድሜ የሚወስነው የእኛ ጥንካሬ ነው። የጥንካሬያችን መሰረቱ አንድነታችን ነው። ወሎ ብቻውን ምንያደርጋል? ጎጃም ሲጨመር ይጠነክራል፤ ሸዋ ሲታከል ላይበጠስይገመዳል፤ ጎንደር ሲጨመር አንድነታችን አንበሳ ያስራል፡፡ አንድነት የድላችን ቁልፍ ነው፤ ለዚህ ነው የመላው አማራ አባትብ/ጀነራል አሳምነው ጽጌ አንድ ሁኑ ብሎ የድላችንን ቁልፍየነገረን፤ አንድ ሁኑ እንደተባልን አንድ እንሁን እያልን አማራዊ ጥሪያችንን እያቀርብን በዓሉን ለምታከብሩ የሰው ልጆች ሁሉ በዓሉ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የመተሳሰብ እንዲሆን ኮራችን መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡  

መልካም የገና (የልደት) በዓል!
የአማራ ፋኖ በወሎ ላስታ አሳምነው ኮር

Ethio 251 Media

06 Jan, 17:32


በአማራ ፋኖ በወሎ ከላስታ አሳምነው ኮር የልደትበዓልን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ!

በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላውዓ ለምለምትገኙ የክርስትናእምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችንና ለመድሃኒታችንኢየሱስ ክርስቶስ እና ለፃዲቁ ንጉስ ቅዱስ ላሊበላ የልደት በዓልበሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!

የጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ተስፋ እውነትመሆን የጀመረበት፣ ቃለ መለኮት ሰው የሆነበት፣ ጌታችንናመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ሁሉ ድህነት ይሆን ዘንድወደ ምድር የመጣበት የመጀመሪያዋ የምስራች (ወንጌል) ናት፡፡ ልደቱም ለነቢያት የትንቢታቸው እውነት፣ ለሰባሰገል የፍለጋቸውግኝት፣ ለእረኞቹ የእምነታቸው ንፅህና፣ ለመላእክትና ለሰው ልጆችህብረ ዝማሬ፣ ለዓለም ሁሉ ድህነት የሆነበት ታላቅ በዓል ነው፡፡በመወለዱም የጥንት ጠላታችንን የዲያቢሎስን ቀንበር ከጫንቃችን አነሳልን፤ በሞት ጥላ ሥር ለነበርን ሁሉ ብርሃንን አሳየን።  

አማኑኤል በልደቱና በሞቱ ከጨለማው ገዥ ባርነት አርነት ያወጣን በዋጋ የተገዛን ህዝቦች ብንሆንም የጨለማው ገዥ አምሳያዎች ዛሬም በምድራዊ ህይዎታችን የአፓርታይድ ቀንበር ጭነውብናል።

ከትውልዱ ሁሉ ፋኖ አስተዋለ፤በእሱና በወገኑ ላይ የተጫነብንን የሞት ቀንበር ለመሰባበር ተሰለፈ። የፋኖ ትግልለአማራው ብሎም ለመላው የሃገራችን ህዝብ የተስፋ ብርሃንየፈነጠቀ፣ ከአፓርታይዱና ከሰልቃጩ አገዛዝ የፍዳ ቀንበር፣ሰቆቃ፣ ግድያ፣ከስርዓት ሰራሽ ርሃብና ድህነት፣ ከአፈና፣ ከእገታ፣ከአፈሳ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ሀገረ መንግስት የመፍረስ አደጋመትረፊያ መንገድ አድርገው የሚጠብቁት፣ እራሱን ለዚያ ያጨእና የሚበቃት ትግል ነው፡፡
የላስታ አሳምነው ኮር የተቆጣጠርናቸው አካባቢዎች የጌታችንናመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አማኑኤል የልደት በዓል በድምቀትየሚከበርባቸው ቦታዎች መሆናቸው ይታወቃል።

በመሆኑምየአካባቢው ማህበረሰብ እና ከተለያዩ የሃገራችን እና የዓለም ክፍልየሚመጡ እንግዶች በዓሉን በሰላም እና በተረጋጋ መንፈሳዊፅሞና እንዳያከብሩ ጨፍጫፊው እና ዘራፊው የአገዛዙ ጦርበከባድ መሳሪያዎች እየታገዘ ያለ የሌለ አቅሙን በማሰባሰብበኩልመስክ፣ በድብኮ እና በገለሶት አካባቢዎች ተደጋጋሚ ማጥቃቶችን የሰነዘረ ቢሆንም በክንደ ብርቱዎቹ የአሳምነውልጆች በተቀናጀ ፀረማጥቃት ተመትቶ ሙት እና ቁስለኛውንሰብስቦ በተለመደ ኦነጋዊ ባህሪው ያገኘውን ንፁሃንን እየገደለ፣ የህዝብ ሀብትና ንብረትን በመዝረፍ የቀረውን በማቃጠልመደበቂያ ዋሻ ወደ አደረጋት ላሊበላ ከተማ ተመልሶ ገብቷል፡፡

የአገዛዙ ሰራዊት በኮራችን ላይ ትንኮሳዎችን እየፈፀመ ለጦርነት እየጋበዘን ቢሆንም እሱ በከፈተልን መንገድ ሄደን ታላቁን በዓልና ቅዱሱን ቦታ የጦር አውድማ ላለማድረግ ታግሰናል። የትንኮሳው ዓላማ የምሰጠውን መልስ ሰበብ በማድረግ ከመላው የዓለምክፍል በመጡ ንፁሃን ላይ ጉዳት በማድረስ በዓሉን ለማርከስ እና ቅዱሱን ቦታ ጥላሸት ለመቀባት ያሴረው ተንኮል መሆኑን በመረዳት ሰራዊታችን ምንም አይነት መልስ እዳይሰጥ በማድረግ ሴራውን አክሽፈን ከመላው ዓለም በዓሉን ለመታደም እና የአምልኮ ስርአት ለመፈፀም የመጡ እንግዶቻችንን ሰላምለመጠበቅ የጠላትን ሴራና ተንኮል ቀድመን በመረዳትናበማክሸፍ በዓሉ በሰላም እና የቦታውን ክብር እንደጠበቀ እዲያልፍ እያደረግን እንገኛለን፡፡

በተያያዘም ሰራዊታችንበተቆጣጠራቸው በዓሉ በሚከበርባቸው ቦታዎች ማለትምብልባላ ጊዮርጊስ፣ ብልባላ ቂርቆስ፣ ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ሳርዝና ሚካኤል፣ ቀንቀኒት ሚካኤል እና ገነተ ማርያም አካባቢዎች የመጡ እንግዶቻችን ከአካባቢው ህዝብ ጋር በመሆንፍፁም ሰላማዊ እና አስደሳች በሆነ መልኩ እዲያሳልፉ እየሠራን እንገኛለን፡፡

የጀመርነውን የህልውና ትግል በአጠረ ጊዜ በድል አድራጊነት ለማጠናቀቅ አቅደን እየሠራን ሲሆን በዚህም አመርቂ ርምጃዎችን እየተጓዝን እንገኛለን። ትግሉን በአጭር ጊዜ በመቋጨት አገዛዙ በተለይም በሴቶች፣ በህፃናትና በአረጋውያን ላይ እያደረሰ ያለውን ጭፍጨፋ፣ እንግልትና ጦርነት ወለድ መታወክን ታሪክ አድርጎ ወደ ሰላማዊ ህይዎት ለማሸጋገር የሁሉንም የህልውና ትግሉ ባለድርሻ አካላትን (የፋኖንና የሲቪል ማህበረሰባችንን) ተሳትፎንና ትኩረትን ይሻል። ስለሆነም የላስታ አሳምነው ኮር በአራቱ  ጠቅላይ ግዛቶች ለምትገኙ የፋኖ አደረጃጀቶች እንዲሁም ለአማራ ህዝብ እና ለህልውና ትግሉ ደጋፊ ኢትዮጵያውያን በሙሉ የሚከተሉትን ሁለት ጥሪዎች እናቀርባለን።

1ኛ/ በአራቱም ጠቅላይ ግዛት ለምትገኙ የፋኖ አደረጃጀትከፍተኛ አመራሮች በሙሉ፡-

ከልደት በዓል እንደምንረዳው ጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስክርስቶስ ዘመነ ፍዳን ለማሳለፍ ወደዚች ምድር መምጣትና ዝቅብሎ ክብሩን አውርዶ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖመለኮትን እና ሥጋን አንድ እንዳደረገ ቅዱሱ መጽሐፍ ይነግረናል፡፡ በመወለዱም የምድራችን የመከራ ዘመን ማብቂያ መጀመሪያያሳየን ተስፋ ነበር፡፡ እኛም በሁሉም ጠቅላይ ግዛቶች የምንገኝከፍተኛ የፋኖ አመራር የህዝባችን የፍዳ ዘመን ማብቂያማብሰሪያና በዘላቂነት ዋስትና የሚሰጠውን አንድ አማራዊድርጅት መውለድ ዐብይ ተግባር መሆኑን አውቀን በፍጥነትአንድነቱን እንውለድ ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

አንድነት ማንም ሰርቶ የሚሰጠን ስጦታ አይደለም፤ አንድነት ጥረትንይጠይቃል፤ የእውነት የህዝብ ፍቅርን ይጠይቃል፤ የእውነትለህዝብ መቆምን ይጠይቃል፤ የእውነት እንደ ኢየሱስ ዝቅ ማለትን ይጠይቃል፤ የእውነት መስዋዕት መሆንን ይጠይቃል፤ አንድነት የዓላማ ፅናት ይጠይቃል፤ አንድነት የዓላማ ጥራት ይጠይቃል፤ በመሆኑም የህዝባችንን የፍዳ ዘመን ለማሳጠር፣ የመከራ ቀንበሩን በፍጥነት ለመስበር ሁላችንም ለአንድነት ቅን እንሁን፤ እራሳችንን ዝቅ እናድርግ፤ እንተማመን፤ እንተባበር፤ የጋራግባችንን እናስቀምጥ፤ ችግራችንን የቱ ጋር እንዳለ አብረንእንፈልግ፤ በጋራም ፈትተን አንድ ሆነን ይህንን ተስፋ የተጣለበትንትግል እና ለድል ተጠባቂ የሆነውን ትግላችንን የምናሳካበትየድላችንን የመጨረሻውን መጀመሪያ ተስፋው አድርጎለሚጠብቀን ህዝብ እንድናበስር ስንል ጥሪ እናቀርባለን።

2ኛ/ ለመላው የአማራ ህዝብ እና ለመላው የፋኖአደረጃጀት ደጋፊዎች፦

ሁላችንም ልናውቀው የሚገባን ለውጥ የሁላችንም ተሳትፎናሥራ ውጤት መሆኑን ነው፡፡  ፋኖ የትግሉ ፊት አውራሪ ቢሆንም ብቸኛ የትግሉ ባለቤት አይደለም፤ በየትኛም ቦታ የሚገኝ የዚህትግል ደጋፊ አማራ የትግሉ ባለቤት ነው፤ ለፋኖ ትግል እውቅና የምትሰጡ እና ድጋፍ የምታደርጉ በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የትግሉ ባለቤት ናችሁ ብለን እናምናለን።

በትግል ባለቤትነት ከተማመንን አንድ አማራዊ ድርጅት ለመፍጠር ለሚደረገው ትግል ሁሉም የትግሉ ባለቤትየድርሻውን መወጣት አለበትም ብለን እናምናለን።

ይህም ማለት አንድ መሆን አይችሉም ከሚል ተስፋ አስቆራጭ ንግግር ጀምሮ እስከ ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ ከሚል በሃገራችን የተቃዋሚ ጎራውታሪክ ትልቅ ኪሳራ ሲያደርስ ስከነበረው አስተሳሰብ እንደ ህዝብመላቀቅ አለብን፡፡ አድነት የተወሰኑ አካላት ሰርተው የሚያለብሱንሳይሆን አብረን የምንገነባው አንድ አማራዊ ቤት ነው፡፡

በመሆኑም የህልውና ትግላችን ባለድርሻ ሁሉ እንደ ትግል ባለቤትግድፈቶችን የሚያመላከት፣ አጥፊዎችን የሚገስጽ፣ ተራማጆችንና ሃቀኞችን የሚተባበር እና አብሮ የሚሰራ የትግሉ ጠባቂ መሆን መጀመር አለበት ስንል ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

Ethio 251 Media

06 Jan, 17:06


ከአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የገና በዓልን አስመልክቶ የተሰጠ የእንኳን አደረሳችሁ መግለጫ!

እንኳንስ የክርስቶስ ኢየሱስ የልደት በዓል ዋዜማ ላይ ሁነን ይቅርና በዘወትር ቀናትም ቢሆን እንዴት ዋላችሁና ከረማችሁ ከአፋችን የማይለይ ብቻ ሳንሆን እግዚአብሄር ይመስገን… ያውም በነገር ሁሉ ብለን ባለቤታችንን እንደምናውቅ አስረግጠን የምንናገር ፍጡር ነን፡፡ ትልቁን ነገር ይዘናል… አለምም በዚህ ያውቀና፡፡

በመሆኑም እንናተ የአማራን ህዝብ ከብሄር ተኮር ጥቃት ለመታደግ በዱር በገደል የምትንከራተቱ፣ በማንነታችሁ ብቻ የእለት ተእለት ሰቆቃና እንግልት የምትቀበሉ፤ ሀብትና ንብረታችሁ ተዘርፉ በየ-ስደት ጣቢያዎች ለምጽዋት ኑሮ የተዳረጋችሁ፤ ግፍና በደል ይብቃ በሚል ሲቃ ስላሰማችሁ በየ እስር ቤት ታጉራችሁ ቁም ስቅል የምታዩ፤ ብሎም ከዛሬ ነገ ምን ይመጣብን ይሆን በሚል በጭንቀትና ስጋት የቀን ጨለማ የዋጣችሁ እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በአል አደረሳችሁ፡፡ የጌታችን የመድሀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደትን ስናስብ በልደቱ ምክንያት ብዙ ሀይማኖታዊና ማህበረሰባዊ ጥያቄዎች እንደሚኖሩ በማስታወስ ነው፡፡ በልደቱ እርቅ፣ ሰላም፣ ቂም-የለሽነትና የመዳን ተስፋ ይዘን ማክበር ይኖርብናል፡፡ በዚህም ለእኛ የትግል ጉዞ ብዙ አስተምሮት ያለዉና መካሪና አቅጣጫ አመላካች አንድምታ ያለው በአል አድርግን እንወስደዋለን፡፡ ክርስቶስ እኛን ያድን ዘንድ ወደ ምድር እንደመጣ ሁሉ እኛም የአማራን ህዝብ ለማዳን ወደ ዱር ገብተናል፡፡

በጌታ የትውልድ ጊዜ የእስራኤል አካል በነበሩ የገሊላና የይሁዳ ክፍለ ሀገራት መካከል ከፍተኛ አለመግባባት ነበር፡፡ ነገር ግን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገሊላ ተጸንሶ በይሁዳ በቤተ-ልሄም ግርግም ሲወለድ በሁለቱ አዉራጃዎች መካከል የነበረዉን አለመግባባት ከንቱ አድርጎ ሽሮታል፡፡
በሌላ በኩል የክርስቶስ ልደት ሰው ከአምላኩ እንደታረቀ የተበሰረበት ብቻ ሳይሆን ከጠላቱ ከዲያብሎስ ለዘላለም እንደተለየ ማሳያ እለትም ነበር፡፡ በአንድ በኩል በሰውና በአምላክ መካከል የነበረው የጥል ግድግዳ እንደሚፈርስ የተረጋገጠበት የመጀመሪያው የተግባር ምእራፍ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ከሰይጣንና ሰራዊቱ ጋር ለዘላለም የሰው ልጅ እንደማይገናኝ የልዩነት ግድግዳ የጸናበት ጊዜም ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሰይጣን ወደ ጥልቁ ሊጣል እንደቀረበ አንዱ የተግባር ማረጋገጫ እለት ነበር፡፡ ለዚህም እኮ ነው ዲያብሎስ በሄሮድስ ልቦና አድሮ ያን ያህል ንጹሀን ህጻናትን እንዲፈጅ ያስደረገው፡፡ ልክ ዛሬ በአብይ አህመድ አድሮ አማራን እንደሚያስጨፈጭፍ ማለት ነው፡፡

ይህ ሁኔታ ከእኛ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል፡፡ ዛሬ ያለንበት ነባራዊ ሀቅ አንድነታችንን እያጠናከርን ብሎም ለዘላለም እንዳይናጋ መሰረት እየጣልን ብቻ ሳይሆን ያለያየንን የፀብ ግድግዳና ግድግዳ መሳይ ነገር እየናድን ጎርባጣውን ገደላ-ገደል ደልዳላ እያደረግን ምቹ የሩር-መለጊያ ሜዳ እየፈጠርን ነው፡፡ በክርስቶስ ልደት በጭራሽ ከሰይጣን ጋር እርቅ እንደሌለ ሁሉ እኛም ከሰው ዘር-አጥፊ ጋር የሚያገናኘንና የሚያስማማን አጀንዳ እንደሌለ አስረግጠን በድጋሜ እንናገራለን፡፡

ክርስቶስ በሰውና በዲያብሎስ መካከል ያቆመው ግድግዳ በአማራ ህዝብና በአብይ መራሹ መንግስት መካከልም በጽኑ ቁሟል፡፡ ሰይጣን የሰውን ልጅ ሊያጠፋ እንደመጣ ሁሉ አብይ አህመድ አማራን ለማጥፋት ተነስቷል፡፡ ክርስቶስ የሳጥናኤልን መንግስት እንዳፈራረሰ ሁሉ ፋኖም የአብይን መንግስት ያፈራርሰዋል፡፡ ሰላም የሚገኘውም ከሰይጣን በመታረቅ ሳይሆን የሚከፈለውን ዋጋ ሁሉ በጽናት ከፍሎ በማሸነፍ ብቻና ብቻ ነው፡፡ ለዚህም ነው ክርስቶስ እስከ መሰቀል መስዋእትነትን የከፈለው፡፡

በሌላ በኩል የገና በአል ለእኛ ትግል የሚያስተምረው ሌላዉ ነገር የወንድማማች ቂምን መሻር ነው፡፡ ክርስቶስ ወደዚህ ምድር የመጣው እኛን ስለበደለን ይቅርታ ሊጠይቅ ሳይሆን እኛ በዳዮቹን ሊምር ነው ያውም እራሱን አሳልፎ እስከ ሞት ድረስ በመስጠት፡፡ የእኛም ስርአት ይህን የተከተለ መሆን አለበት፡፡

ትናንት ከፋፋዮች ሲለያዩን በገባነው ግጭት የተፈጠረ ብዙ ነገር ይኖራል፡፡ ነገም ከእርቅ በኋላ ያንን በደል ሽረን… እንዳልነበር ቆጥረን በአዲስ መንፈስና ወኔ ወደፊት ልንጓዝ እንጂ እንደ-ከብት የተዋጠን እየመለስን ልናመነዥክ አይደለም፡፡ መከባበር፣ መዋደድ፣ በእኩል መተያየትና ይቅር መባባል በውስጣችን መንገስ ይኖርበታል፡፡ በገና የአጨዋወት ስርአታችንም እኮ “በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” ሲል እኩል ነን፣ አንድ ነን፣ ይቅር እንባባላለን ብሎም የፍቅር ቀን ነው ብሎ ሲያጠይቅ ነው፡፡ የእኛ የትግል ዘመንም ይሄው ነው፡፡

ህዝባችን ምን ያህል እንደተዋረደ፣ እንደተናቀ፣ እንደተጎሳቀለና ተስፋ የሌለው ፍጡሩ እስኪመስል እንደተገፋ ታውቁታላችሁ፡፡ ነገር ግን ምንም ያልተጠበቀችውንና እንደ ተናቀች የተቆጠረችውን የናዝሬትን ከተማ ኢየሱስ እንዳከበራትና ብዙ ብዙም እንዳደረገላት እኛም በሙሉ ልብ ይህንን የጽልመት ጊዜ እንሻገረዋለን፡፡ በብርሀንም እንተከዋለን፡፡ የግፉ መሙላት፣ የዋይታ መብዛትና የበዳዮች ትእቢት ከፍ ከፍ ማለት ጠላቶቻችን የመውደቅ አፋፍ ላይ ለመሆናቸው ማረጋገጫ ነው፡፡ ሊነጋ ሲል ይጨልማልና!

"ድላችን በክንዳችን"
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የህዝብ ግንኘነት ክፍል

ታህሳስ 28/2017 ዓ/ም
ሸዋ አማራ ኢትዮጵያ

Ethio 251 Media

06 Jan, 17:03


አርበኛ ኮማንዶ ሳሙኤል ባለድል
ከአማራ ፋኖ በጎንደር ም/ሰብሳቢና ወታደራዊ አዛዥ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የተሰጠ መግለጫ

Ethio 251 Media

06 Jan, 16:17


ክርስቶስ የሰውን ልጆች ሁሉ ለማዳን እደተወለደ ለእኛም ለአማራዎች የፋኖ ትግል ተወልዶልናል !!

ለተከበርከው ታላቁ የአማራ ህዝብ ፣በውጪም በሀገር ቤትም ያላችሁ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ2017 ዓ.ም ለጌታችን ለመድሀኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በፅናት አደረሳችሁ አደረሰን ።

እንደሚታወቀው አሁን ያለንበት ወቅት የአማራ ህዝብ በፋሽስት አምባገነኖች የጥፋት ጦርነት ታውጆበት ፤በዘመኑ አሉ በተባሉ መሳሪያዎች ከምድር እንዲጠፋ በብዙ ተዋናዮች ጅምላ ፍጅት እየተፈፀመበት ይገኛል። ሆኖም እደሚታወቀው ቆራጥ የአማራ ልጆች እንደህዝብ የተደቀነብንን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ ክርስቶስ ራሱ በፈጠራት አለም ውስጥ ለጠፋው ለሰው ልጅ በከብቶች በረት እደተወለደ ሁሉ ፤የአማራ ህዝብ በፈጠራት ሀገር ውስጥ ተሳዳጅና ባይተዋር በመሆኑ ከፈፅሞ ጥፋት ለማዳን የቁርጥ ቀን ልጆች ጫካ ከገቡ ሁለት አመታት ተቆጥረዋል ።

በታሪክ እንዳየነው ክርስቶስ ከውልደት እስከ ስቅለቱ ባሳለፋቸው ዘመናት ውስጥ የተበላሸ ስርዓትን ለመለወጥ ምን ያህል ፈታኝ ዋጋ እደሚያስከፍል ከቅዱስ መፀሀፍ አንብበናል ።

እኛም ይህን በዓል ስናከብር አባቶቻችን የሰጡንን ጠቃሚ እሴቶችን በመጠበቅ ጎጂ የሆኑ የኛን እሴቶች ሊያጠፉ የሚችሉ ባዕድ የሆኑ ልማዶችን በማስወገድ የራሳችንን እምነት (faith) ማስቀጠልና መጠበቅ አማራዊ የትግል ግዴታችን ነው ።

ለዚህም በዓሉን ስናከብር ሊተገበሩ የሚገባቸውን መመሪያዎች እደሚከተለው እገልፃለን።

፩.በተቆጣጠርናቸው አካባቢዎች ህዝብና በዓሉን ሊረብሹ የሚችሉ የደስታ ተኩሶች ፣ ከልክ ያለፉ የአልኮል መጠቀምና ማወክ ክልክል ናቸው።

፪.በቅርብ ልምድ የመጡ የገና ዛፍ ፣የገና አባት የሚሉ ከአማራ ሕዝብ ማህበራዊ እሴት ዝምድና የሌላቸውን ባዕድ ባህሎች ከማስፋፋት መቆጠብ።

፫.ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ሁሉ ያላችሁ የጎበዝ አለቆች ከህዝባችን ጋር ተባብራችሁ የአካባቢያችሁን ፀጥታውን እድታስከብሩ !!

፬.በዓሉን ስናከብር በየአካባቢው የሚገኙ አቅመደካሞችን በመጠየቅና በመረዳዳት እድናሳልፍ!!

፭.ሁሉም ክፍለጦሮች በማዕከላት ያሉትን የተማረኩ የጠላት ሰራዊት አባላት አቅም በፈቀደ መጠን በዓሉን ደስተኛ ሆነው በጋራ እንዲያሳልፉ ያሳስባል !!

፮. እንዲሁም በህልውና ትግሉ ውስጥ ሲታገሉ የቆሰሉና የተሰው ፋኖ አባሎችና ቤተሰቦችን በመጠየቅና በማፅናናት እንድታሳልፉ አማራዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መልዕክቱን ያስተላልፋል!!

ድል ለአማራ ህዝብ !!
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት !!

አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ !!

ታህሳስ 2017 ዓ.ም

ሸዋ ፣አማራ ፣ኢትዮጵያ

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 17:31


የዛሬ ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-
https://x.com/i/broadcasts/1ZkKzRbARYyKv

https://rumble.com/v65vbe4--251-january-4-2024-251-zare-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

04 Jan, 17:12


የአማራ ፋኖ አንድነት መንገድ!

ከሸዋ በመነሳት ከተለያዩ የፋኖ መሪዎች ጋር ውይይት እያደረጉ ያሉት አርበኛና ደራሲ ተስፋዬ እና አርበኛ ሽመልስ ንጉሴ ከሰሞኑም ከአርበኛ ድርሳን ብርሃኔና ከይታገሱ አራጋው ለረጆች ጋር ፍሪያማ ውይይት ማድረጋቸውን ኢትዮ 251 ሚዲያ ሰምታለች!

Ethio 251 Media

04 Jan, 15:20


ታላቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መድረክ በዲሲ !!

በአራቱም ቀጠና የሚገኙ የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች ጊዜያዊ የሰብዓዊ ድጋፍ አሰባሳቢ ኮሚቴ ማቋቋማቸው ይታወቃል ። ይህ ኮሚቴ ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር ዲሲ ላይ ለJanuary 12 2025 የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት እያደረገ ነው።

በየትኛውም የአለም ክፍል ለምትገኙ እና ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ ወገኖች ትኬት በonline በመግዛት ማገዝ ትችላላችሁ።

ትኬት ከአንድ በላይ መግዛት ይቻላል።

👇👇👇

https://Help-Amhara-2025.eventbrite.com


https://www.eventbrite.com/e/rehabilitation-fundraising-for-victims-of-war-on-amhara-tickets-1127261833489?aff=oddtdtcreator&fbclid=IwZXh0bgNhZW0CMTEAAR3yxaLx3Tv8uvDqLzD6A7wbc0RsSuGRePKnfnebxVNxk1e0GYE6JAJE0bo_aem_ZDdu4dbZaqSLom1qjQbt1A

Ethio 251 Media

04 Jan, 14:19


"በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት አባላት የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝን ተቀላቀሉ!

ታሕሳስ 26/2017 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ

በሸዋ ግንባር በበርካታ ቀጠናዎች በተደረገ አውደ ውጊያ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት ሲደመሰስ ፤ አገዛዙን የተጠየፉና በአማራ ፋኖ ሀቀኛ ትግል ያመኑ ስርዓቱን ከድተው የወገን ጦርን ተቀላቅለዋል።

በገጠመው ግንባር በሙሉ ሽንፈት የሚደርስበት የብልፅግና አገዛዝ ፤በቂ ወታደራዊ ስልጠና ያልወሰዱ ፣ እድሜያቸው ለውትድርና ግዳጅ ያልረሱ ወጣቶችን ከተለያዩ ከተሞች በማፈስ በግዳጅ አሰማርቶ በየሜዳውና በየጫካው እንዲወድቁ እያደረጋቸው ይገኛል። ከሰሞኑ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ሁሉም ክፍለ ጦሮች በጠላት ሠራዊት ላይ በወሰዱት የተቀናጀ እርምጃም ለቁጥር የሚታክት የብልፅግና ሠራዊት ተደምስሷል።

በዚህ ከፍተኛ ድል በተመዘገገበበት አውደ ውጊያ ከመደምሰስ የተረፉት ምርኮ ሲደረጉ ፤ የተቀሩት ደግሞ ከሰላድንጋይ ከተማ ወደ ሳሲት በመሄድ !! እጃቸውን ለወገን ጦር አስቻለው ደሴ ክፍለጦር በሰላማዊ መንገድ እጅ በመስጠት :-

👉 2- ስናይፐር
👉 11-ጥቁር ክላሽንኮቭ እና
👉 4 -ዘመናዊ ምሽግ መደርመሻ ኢነርጋ ይዘው

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የተቀላቀሉት የሠራዊት አባላትንም የምርኮኞች አያያዝና ጥበቃ ክፍል ተረክቦ በቂ እንክብካቤ እያደረገላቸው ይገኛል።

በሸዋ 9ኛ ቀኑን የያዘው አውደ ውጊያ ዛሬም በተለያዩ ግንባሮች የቀጠለ ሲሆን ከፍተኛ ተጋድሎ ትንቅንቅ በማድረግ ላይ ይገኛል። "

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል

Ethio 251 Media

04 Jan, 13:50


የአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ግብስብስ ሰራዊት ፋኖ በሌለባቸው ቀበሌዎች ጥቁር አስፓልትን ተከትሎ ሳማ ሰንበት ቀበሌ ቤት ለቤት በመግባት ለእንግዳ ክብር ያለውን ደግና ገራገሩን ለተራበ አጉራሹን ለተጠማ የሚያጠጣውን ለታረዘ የሚያለብሰው ያን ደጉን የአማራ ህዝብ ዘር ማንዘሩን ለማጥፋት ጨካጩ ግልገሉ ሂትለር አብይ የሄደበት የሞከረው መንገድ ሁሉ ውጤት አልባ ሆኖበት ፋኖ መንግስት እዬሆነ መንግስት ተራ ሌባና ወንበዴ ከሆነ ሰነባብቷል ።

የአለማችን ጨካኙ ሂትለር በስንት ጣሙ ምናልባትም የዘመናችን የቅርብ የሶሪያው ጨካኙ አሳድ አልበሽር  በስንት ጣሙ የሚያስብለው የጥልቁ አውሬ መናፍስቱ ንጉስ አብይ ወንጀሉ ወደር የለውም።

ያ በላብ በወዙ አርሶ አለስልሶ አለምን የሚመግበው የአማራን ህዝብ ሀገረ መንግስት አፅንቶ ስልጣኔን ለአለም ባስተዋወቀ አብይና ሎሌዎቹ እንዲጠፋ የፈረዱበት የአማራ ህዝብ በቆራጥ ልጆቹ በአማራ ፋኖ እስትንፋሱ እየቀጠለ ይገኛል።

የጥቁሩ ሂትለር አብይ ሰራዊት የሽንፈቱን ካባ መከናነብ ሲሳነው በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ ከሰሞኑ በክንደ ብርቶቹ ነበልባል ፋኖች እጅጉን ሲመታ የደጉን አርሶ አደር  በውድማ የተከመረ ጤፍና የእንሰሳት መኖ ጭድ በሳት ማቃጠሉ ጥቁር ሂትለር አብይ የሚለው ስም ሲያንሰው እንጂ አይበዛበትም።

የጥቁሩ ሂትለር አብይ አገዛዝ አረመኔ ሰራዊት በቀን 25/4/2017 ዓ.ም ጥቁር አስፋልት በመከተል ወደ ሳማ ቀበሌ በመግባት ቤት ለቤት ሌማት እዬገለበጠ የበላውን በመብላት የተረፈውን በመድፋት ወራዳነቱን አስመስክሯል።

ለህዝቡ ሠላም አስከብራለሁ የሚለው ዲስኩራሙ የገለማ የፖለቲካ ባለቤቱ አብይ ሰራዊቶቹ ሳማ ቀበሌ ወልደአረጋይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ አንዲን ሴት ለመድፈር አስበው ስታስቸግር ክፉኛ በቡድን በመደብደብ ለከፍተኛ ስነልቦናዊና አካላዊ ጉዳት ዳርገዋት ለህክምና ወደአረርቲ ብትላክም ከአቅም በላይ ሆኖ እሪፈር ተብላለች ።

ግለሰቧ ከጣት ቀለበቷ ጀምሮ ያላትን ጥሬ ገንዘብና ጌጣጌጦች በሙሉ በአገዛዙ ሰራዊት ተዘርፋለች።

በተመሳሳይ በዚያው ቀበሌ ቁጢሱ አገር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ ግለሰብ ልማት ውስጥ በመግባት ከዛሬ ነገ ደረሰልኝ እያለ የሚጠባበቀውን ሸንኮራ አገዳ ልማት ሙሉ በሙሉ አውድመዋል።

በዚያው ቀበሌ የበልግ ሽንብራ በአበባ ላይ ያለ ዥንጀሮ እንኳን አለመሸቱን አይቶ የማይነካውን አበባ ላይ ያለን ሽንብራ በመነቃቀል አውድመዋል። 
ይህን ፀያፍ ተግባር ከፈፀሙ በኋላ የፋኖን ወደ አካባቢው በፍጥነት መምጣት የሰሙት አረመኔዎቹ የአብይ ሠራዊት አካባቢውን ለቀው ወጥተዋል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለ ጦር ነበልባል ብርጌድ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዳያ ገልጿል።

Ethio 251 Media

04 Jan, 13:48


የአገዛዙ መንኮታኮት

የአብይ አገዛዝ በአማራ ብዓዴናዊያን የገለማ የፖለቲካ ትርክታቸው ''ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ'' በሚመስል የምኞት ተረት ጃውሳውን ደመሰስሁ ነፍጠኛ እጅ ሰጡኝ እያለ እመሬት በሌለ የውሀ ሽታ ዲስኩር በሞርተር በዙ-23 በመድፍና ታንክ በምድር በንፁሃን ሀብትና ነፍስ ሲጫወት በሰማይ ድሮን እና ተዋጊ ጀቶችን በማዋሀድ በሰላማዊ ዜጎች ሲያዘንብ በዚህ ከባዕዳን ሀገር የተጋጨ በሚመስል መልኩ እገዛሀለሁ ሰላም እሰጥለሁ በሚለው ህዝቡ የተጠቀሱትን መሣሪያ ሲያርከፈክፍ ቢሰነብትም ፋኖ ወደፊት መግፋቱን ምንም ምድራዊ ሀይል ሊገታው ሊያስቆመው አልቻለም በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለ ጦር ነበልባል ብርጌድ
ፋኖ በሚንቀሳቀስባቸው 28 ቀበሌዎች ውስጥ አንድም ፋኖ ተማርኮም እጅም ሰጥቶ አያውቅም።

በተገላቢጦሽ በሃምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን ዋና ጦር አዛዢነት የሚመራው የክንደ ብርቶቹ እንደ አመድ እሳት የሚፋጁት ነበልባሎቹ አገዛዙን በግንባር ውጊያ በሽምቅ ምሽግ በመግባት ከምሽግ በማሶጣት አመናምነውታል ።
ነበልባሎቹ የአገዛዙን ሰራዊት ሲሻቸው በማስከዳት ይገረምዱታል በቀን 25/4/2017ዓ.ም የነበልባሎቹ  ሺአለቃ ሁለት እረመጦቹ ቴድሮስ ሺ አለቃ ሁለት ቀጫጭኖቹ ፋኖች አረርቲ ከተማ ሰርገው በመግባት ከከተማው ለመውጣት ሁኔታው አልመቻች ያለውን ሚኒሻ ከነሙሉ ትጥቁ ከምሽቱ 3:10 አካባቢ ይዘውት ወደ ፋኖ ቀጠና ወስደውታል።

የአገዛዙ አገልጋይ ሚሊሻዎችም ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ እርስ በእርሳቸው በመታኮስ የተመታቱ ሲሆን ቅጥረኛው በፍቃድ ሞገስ በከፈተው ተኩስ ውታፍ ነቃዩ ሚኒሻ አለም ተመቶ በህክምና ይገኛል ሚሊሻው እየተባላ ነው።

ድል ለአማራ ፋኖ!!!
ነፃነታችን በክንዳችን!!!

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር የነበልባል ብርጌድ ፋኖ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል።

Ethio 251 Media

04 Jan, 13:37


በማዕከላዊ ጎንደር እየተደረጉ ያሉ ድሎችና እየተገኙ ያሉ ድሎችን በተመለከተ ከቀጠናው የፋኖ መሪዎች ጋር የተደረገ ቆይታ!

Ethio 251 Media

04 Jan, 13:36


በደቡባዊው ጎንደር ቀጠና እየተደረጉ ባሉ ተጋድሎዎች ከፋኖ አመራሮች ጋር የተደረገ ቆይታ!

Ethio 251 Media

04 Jan, 13:15


የኢትዮጵያ ካናዳዊያን ኔትወርክ ለማህበራዊ ድጋፍ ከወሎ ቤተ-አማራ የበጎ-አድራጎት ማህበር ጋር በመተባበር በሰሜን ወሎ አይና ቡግና ወረዳ ለተከሰተው ረሃብ ጊዜያዊ ድጋፍ አደረገ።

የበርካቶች ተሳትፎና የድጋፍ ትብብር የሚፈልገው የቡግናው ርሀብን የኢትዮጵያ ካናዳውያን ከወሎ ቤተ-አማራ ማህበር ጋር በመተባበር ድጋፍ ማድረጉን ለኢትዮ 251 ሚዲያ ባደረሰው መረጃ አስታውቋል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 12:45


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አበበ ሙላት ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት .....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 12:40


የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ጎቤ ክፍለጦር ቃልአቀባይ ፋኖ መምህር አስፋው አደራጀው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት .....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 12:32


በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት አባላት የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝን ተቀላቀሉ!

በሸዋ ግንባር በበርካታ ቀጠናዎች በተደረገ አውደ ውጊያ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት ሲደመሰስ ፤ አገዛዙን የተጠየፉና በአማራ ፋኖ ሀቀኛ ትግል ያመኑ ስርዓቱን ከድተው የወገን ጦርን ተቀላቅለዋል።

በገጠመው ግንባር በሙሉ ሽንፈት የሚደርስበት የብልፅግና አገዛዝ ፤በቂ ወታደራዊ ስልጠና ያልወሰዱ ፣ እድሜያቸው ለውትድርና ግዳጅ ያልረሱ ወጣቶችን ከተለያዩ ከተሞች በማፈስ በግዳጅ አሰማርቶ በየሜዳውና በየጫካው እንዲወድቁ እያደረጋቸው ይገኛል። ከሰሞኑ የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ሁሉም ክፍለ ጦሮች በጠላት ሠራዊት ላይ በወሰዱት የተቀናጀ እርምጃም ለቁጥር የሚታክት የብልፅግና ሠራዊት ተደምስሷል።

በዚህ ከፍተኛ ድል በተመዘገገበበት አውደ ውጊያ ከመደምሰስ የተረፉት ምርኮ ሲደረጉ ፤ የተቀሩት ደግሞ ከሰላድንጋይ ከተማ ወደ ሳሲት በመሄድ !!  እጃቸውን ለወገን ጦር አስቻለው ደሴ ክፍለጦር በሰላማዊ መንገድ እጅ በመስጠት :-

👉 2- ስናይፐር
👉 11-ጥቁር ክላሽንኮቭ እና
👉 4 -ዘመናዊ ምሽግ መደርመሻ ኢነርጋ ይዘው

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የተቀላቀሉት የሠራዊት አባላትንም የምርኮኞች አያያዝና ጥበቃ ክፍል ተረክቦ በቂ እንክብካቤ እያደረገላቸው ይገኛል።

በሸዋ 9ኛ ቀኑን የያዘው አውደ ውጊያ ዛሬም በተለያዩ ግንባሮች የቀጠለ ሲሆን ከፍተኛ ተጋድሎ ትንቅንቅ በማድረግ ላይ ይገኛል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 12:26


የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ የአገዛዙ ሠራዊት እንቅስቃሴና የፋኖ ድሎችን በተመለከተ  ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 12:24


የአማራ ፋኖ በጎጃም ቢትወደድ አያሌው ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ይበልጣል የእውነቱ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 12:22


የአማራ ፋኖ በጎጃም ስድስተኛ ክፍለጦር ቀስተደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ፋኖ ኢንጅነር ዘመን ባሳዝነው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

04 Jan, 11:50


የአማራ ፋኖ በጎጃም የ6ተኛ ክፍለጦር ቀስተደመና ብርጌድ ኃላፊ ፋኖ ዘመን ባሳዝነው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Jan, 18:49


ከአማራ ፋኖ በጎንደር የጉና ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የተላለፈ መልዕክት!

****

ሥርዓቱን ያሸነፍን መሆኑን ከበሰበሰው ብልፅግናው ቡድን በኩል ተኳኳለው የሚወጡ መረጃዎችን ማየት በቂ ነው። ሰሞኑን ባደርግናው ተጋድሎ በጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብኣዊና ቁሳዊ ውድመት አድርሰንበታል። ካሸነፍን የሰነበትን መሆኑን ማመን ያልቻለው ቡድኑ ዛሬም ጣረሞት ላይ ይገኛል።

ስርዓቱ ተሸንፏል። የቀረን ነገር ቢኖር ሰኞ በአንድ ቁመና ማክሰኞ ዕለት የድሉን ዋንጫ ማንሳት ብቻ ነው። ከዚህ ላይ እንጠንክር ። የውስጥ አንድነታችንን በማጠንከር የድል ትንሳኤውን እናፋጥን። ድሉን ጠልፎ ለመጣል በውስጣችን የተወሸቁ የጭቃ እሾህ የሆኑ አፈቀላጤዎችን እንለይ።

በጊዜያዊ ጥቅምና በጥላቻ ስርዓቱ እንዲቆይ ትግላችን እና ስብእናችን አሳልፈው የሚሰጡ ስግብግብ አካላት ልንታገሳቸው አይገባም። የበሰበሰው የብልፅግና ቡድን መሰረታዊ የሚባሉትን የሀገራችንን እና የክልላችንን ጥቅሞች ለሽያጭ በሚያቀርቡ አካላት ላይ ፋኖ ጦርነት ወደ ማዎጅ ተሸጋግሮ ይገኛል።

የዚህ ቡድን ሴራዎች ባካሄዳችን
ይሁን በፋኖ ትግል ለጠባብ ፍላጎት ሲባል የህዝባችን ጥቅም ወደ ገደል ገፍትሮ ለመጣል የሚያደርጉትን ማንኛዉንም ነገር ተቀባይነት የለዉም። ይሁን እንጂ ህልዉናችን በጠንካራ ክንዳችን እና በትክክለኛ እዉነቶች የተመሰረተ ስለሆነ ታሪክ እና ትግሉ ምስክር ናቸው።

የገመው ህገወጡ የ‘ብልፅግና’ ቡድን ከድሃ ጉሮሮ እየቀማ ስልጣንን በገንዘብ የመግዛት ተግባር እንዲወገድ የጉና ክፍለ ጦር በፅኑ አቋም ይቃዎማል።

የአማራ ህዝብ በየቦታዉ የጅምላ መቀበሪያ ቄራ ሆኖ ለድርድር እንደማንቀርብ የጉና ክፍለጦር አስምሮበታል።

የተከበርከው የአማራ ህዝብ እና የትግል አጋር አካላት ሆይ አሁናዊ ሁኔታዎችን ተጨባጭ ሁነቶችን በጥሞናና በእውቀት በመመርመር የበሰበሰው የብልፅግና ቡድን የያዘውን የጥፋት መንገድ እንዲያቆም ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ ከህግና ከታሪክ ተጠያቂነት ራሳችሁን እንድታድኑ ጥሪ እናቀርባለን።

የተከበርክው የአለም አቀፍ ተቋም በተለይ ደግሞ ኢጋድ፤አፍሪካ ህብረት እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዲሁም ሌሎች የሚመለከታችሁ አካላት የዘር ማፅዳት ታሪክን የማጥፋትና በአወንታዊ ሚናችሁ ሀላፊነታችሁን እንድትወጡ ጥሪ እናቀርባለን።

ታህሳስ 22/2017 ዓ/ም
የአማራ ፋኖ በጎንደር የጉና ክፍለጦር ዋና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ!
አርበኛ መ/ር ያሬድ ገደፈ

Ethio 251 Media

01 Jan, 16:39


ዛሬ በቀን ታህሳስ 23 2017 ከድጎ የተነሳው ጠላት ዋብርን ለመያዝ በጠዋት ተጠግቶ የነበረ ቢሆንም በጀግኖቹ የመዝገቡ ዋለልኝ ብርጌድ እና በኩችት ባታይ አርሶ አደር ተቆርጦ በሚገባው ልክ ሲቀጠቀጥ ውሏል!

የብርጌዱ ሻለቃ 1 እና የኩችት ባታይ አርሶ አደር አልማ የሚባል ቦታ ፈረስ ቤት መገንጠያ ላይየወራሪውን 2 አይሱዙ እና 1 ፓትሮል እስከ ሰራዊቱ ዶግ አመድ አርገውታል!

ጠላት ዙ23 እና Bm ጨምሮ ከባድ መሳሪያ ሲያስወነጭፍ ቢውልም በንጹሀን ላይ ማለትም መኖሪያ ቤት ላይ ወድቆ 2 ህጻናት ላይ ጉዳት ከማድረስ ውጭ በወገን ሀይል ላይ አንድም ጉዳት ማድረስ አልቻለም!

Ethio 251 Media

01 Jan, 13:38


የፓርላማ አባሉ ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ግጭት እና ጦርነት ባሉባቸው አካባቢዎች ከፍተኛ የሆነ የኢንተርኔት መቋርጥ ላይ ለኢትዮቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጥያቄ አቀረቡ

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የፓርላማ አባል ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ግጭት ባሉባቸው አካባቢዎች የኢንተርኔት አገልግሎት ሲቋረጥ ሰዎች ተንቃሳቅሰው ክፍያዎችን ለመፈጸም ስልሚገደዱ ለግጭቶች አካላዊ ተጋላጭ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

ደሳለኝ (ዶ/ር) በመላ #ትግራይ ለሁለት አመታት፣ #በአማራ ክልል ለአንድ ዓመት እንዲሁም በ #ኦሮሚያ ክልል በከፊል የኢንተርኔትና የስልክ መቋረጥ እንደነር ጠቅሰዋል።

በተጨማሪም የፓርላማው አባሉ በአማራ ክልል ግጭት ሲጀምር የግል ስልካቸው እና ሲም ካርዳቸው እንዳይሰራ መደረጉንና በተቋሙ ለአደጋ መጋላጣቸውን ገልጸው የኢትዮቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ማብራሪያ እንዲሰጡ ጠይቀዋል።

የፓርላማ አባሉ ይህን ያሉት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የኢትዮ ቴሌኮም የሥራ እንቅስቃሴን  ዛሬ በገመገመበት ወቅት ነው።

ዘገባው የአሻራ ሚዲያ ነው

Ethio 251 Media

01 Jan, 13:06


የአማራ ግሎባል ዲያስፖራ ፎረም በሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በተከሰተው መንግሥትና ተፈጥሮ ሰራሽ ርሃብ ለመታደግ ከJan 4 እስከ Jan 18 የገቢ ማሰባሰቢያ እንደሚደርግ ገለጸ።

አስተባባሪዎቹ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላኩት መልእክት፤ ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያንና የወገናችሁ ጉዳትና ሕመም የሚሰማችሁ ሁሉ ከ Jan 4 - Jan 18 2024 በሚደረገው የገቢ ማሰባሰቢያ በመሳተፍ አለኝታነታችሁን እንድታሳዩ ሲሉ ገልፀዋል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Jan, 10:41


"ፖለቲካዊ ግባችንን በመሳሪያ ኃይል ለማሳካት እየጣርን ነው፤ እናሳካዋለንም፤ የኛ ትውልድም ይነግሳል!"

አርበኛ ዘመነ ካሴ
የአማራ ፋኖ በጎጃም ዋና ሰብሳቢ

ሙሉውን ያድምጡት!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Jan, 10:38


በምንጃር ሸንኮራ የተጀመረ ጭካኔ

ከዚህ በፊት በባልጪ የመንግስት ቤት የሚሰጣቸው የነበረው አቅመደካማ የሆኑ ማመልከቻ ፅፈው የቤት ባለቤት ሆነው ቆይተዋል ፥ ሆኖም አሁን የስግብግብ አመራርና ዝፋን አስጠባቂዎች እኝህ ምስኪን የቤት ክራይ እንኳን የመክፈል አቅም የሌላቸው ሰዎች እያፈናቀሉ ሜዳ ላይ በመጣል ለአገዛዙ ዝፋን አስጠባቂዎች ቤቱን እንደ ማበረታቻ እንዲታደሉ ተወስኖ ባልዋሉበትና ያለሃጥያታቸው ሰላማዊ ዜጎች ፋኖን ትደግፋላቹ የሚል የውሸት ሽፋን በመስጠት እንደምትመለከቱት በወረቀቱ ላይ ለሁሉም የቀድሞ የቀበሌ ቤት ባለቤቶች ላይ ደብዳቤ እየተበተነ ይገኛል።

የአማራ ህዝብ ላይ ከቤቱ የማፈናቀል ስራ በዚህ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
በዚህ ግፍ ትእዛዝ በመስጠት እየተሳተፋቹ ያላችሁ ሰዎች ሁሉ (ወገናችሁን አፈናቅላችሁ የቤት ባለቤት የምትሆኑም ጭምር) ከተጠያቂነት እንደማታመልጡ ከወዲሁ መጠቆም እንፈልጋለንደ።

አማራ ፋኖ ሸዋ እዝ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ ሚድያ ክፍል

Ethio 251 Media

01 Jan, 10:27


"ከበርበሬ ስርቆት እስከ ሀብት ውድመት የደረሰው የአገዛዙ አሳፋሪ ተግባር በምንጃር ሸንኮራ"

አገዛዙ ሳምንቱን በክንደ ብርቱዎቹ ፣ በአይበገሬዎቹ፣ በሞት አይፈሬዎቹ  በሀምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን የቁርጥ ቀን ልጆች በነበልባል ብርጌድ የፋኖ አባላት ሲፈልጉ ከምሽጉ ገብተው፣ሲፈልጉ ከምሽጉ አስወጥተው እንደ ጌሾ ሲወቅጡት ፣እንደ ቡና ሲቆሉት መሰንበታቸው አለም ያወቀው ፀሀይ የሞቀው የምድር ሀቅ መሆኑን ከአለም እስከ አለም ፣ ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ የተመሰከረለት ታላቅ አማራዊ ጀብዱ ሆኖ የሳምንቱን ሰበር ዜና ሆኖ ቆይቷል።

"መግደል መሸነፍ ነው"እያለ የሚደሰኩረው አምባገነኑ  አብይ አህመድ ለግብፅና ለሱዳን ያዘጋጀውን ተዋጊ ጀትና ድሮን በሸዋ ምንጃር ሸንኮራ ህዝብ ላይ ተከታታይ ጥቃት ለመፈፀም ቢሞክርም በእምነቱ እና በማንነቱ የፀናው ለራበው አጉራሽ፣ለታረዘ አልባሽ ለከፋው ደራሽ የሆነው ደጉ የምንጃር ህዝብ ግን የሀብት ውድመት ቢያስተናግድም እንዲሞት የተጣለበት የጀት ጥቃት በአገዙዙ ወታደር ላይ አርፎ የምስኪኖችን ሞት ሴረኞቹ ሞተውበታል።

ከሀዲድ ክላሽ እስከ ስናይፐር፣ከብሬል እስከ ዲሽቃ እየያዙ የአገዛዙን ጨቋኝ ቤት እየለቀቁ ወደ አማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ነበልባል ብርጌድ የፋኖ አደረጃጀት የተቀላቀሉ አማራዊያን እና ኢትዮጵያዊያን ቁጥር ስፍር የላቸውም።

ምሰሶ በሌለው ቤት መኖር የሚፈልገው የብልፀግናው ፀረ አማራ ፋሺስታዊ ቡድን ሰሞኑን በምንጃር ሸንኮራ ህዝብ ላይ የከፈተው ሁሉን አቀፍ ጦርነት በአንድ ወራሪ ሉዓላዊ ሀገር የተከፈተ ጦርነት እንጂ አጥንቱን ከስክሶ ደሙን አፍሶ ሀገር መንግስት  የገነባው የአማራ ህዝብ የተሰነዘረ አይመስልም።

ታህሳስ 21/2017 ዓ.ም አገዛዙ አለኝ ያለውን ተጠባባቂ ሀይል ከየቦታው አግበስብሶ ከታች በእግረኛ፣ በሞርተር፣ በዙ-23 በጄነራል መድፍ ከላይ ደግሞ በድሮን እና በተዋጊ ጀት የተቀናጀ ዉጊያ ቢከፍትም ቀጫጭኖቹ የነበልባል ብርጌድ የፋኖ አባላት ግን እስከ አፍንጫው የታጠቀውን ሌባ ቡድን ሲፈልጉ በቆረጣ ፣ሲፈልጉ በደፈጣ፣ሲሻቸው በከበባ ሲሻቸው ደግሞ በግንባር ዉጊያ ጠላትን ሲያስጨንቁ በዓለም አደባባይ ደግሞ ሲደነቁ ሰነባብተዋል።

     "ሌባ ላመሉ ዳቦ ይልሳል"
ገና ከቤተ መንግስት ሲሸኝ አማራን ዘርፈህ ብላ ተብሎ የተላከው የእነ አብይ አህመድ መጠቀሚያ የብርሀኑ ጁሉ የእንግዴ ልጅ ፣የእነ መካሻ አለማየሁ ማራዘሚያ የፋኖን መብረቃዊ ጥቃት መቋቋም ሲያቅተው በየሰፈሩ እንደ ጅል ውሻ በመልከስከስ ለሞራሉም ለክብሩም ሳይጨነቅ  ሽሮና በርበሬ አንሶላ እና ምንጣፍ ሳይቀር የተወጠረ መጋረጃ እየዘረፈ ፈርጥጧል።

እመረዋለሁ እያለ በውሸት ለሚዘምርለት ህዝብ የማይጨነቀው ስርዓቱ አረርቲ ከተማ ሆኖ ወደ ሸንኮራ አቅጣጫ በሚያስወነጭፈው ጄነራል መድፍ የቤት እንስሳትን ገድሏል የአርሶ አደሩን ጤፍ በገፍ አቃጥሏል።ይህ ደግሞ የእነ መካሻ አለማየውን ከሀዲነት በይፋ ያስመሰክር ይሆናል እንጂ እነ ተመስገን ጥሩነህ፣እነ አብይ አህመድ እንደሆኑ የለየላቸው ፀረ አማራ ከሆኑ አመታትን አስቆጥረዋል።

   "የሚሉሽን በሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ"
አገዛዙ መበተኑን ፣ቀፎ ሆኖ መቅረቱን በግልፅ ለመጠቆም ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም በአማራ ህዝብ ላይ የሚሰራው ግፍ ያማረራቸው፣ የአገዛዙ አካሔድ ያሳቀቃቸው የስርዓቱ አባላት ዲሽቃውን በመፈታታት ዋና ዋና ክፍሉን በመያዝ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለ ጦር የነበልባል ብርጌድን የፋኖ አባላት በክብር ተቀላቅለዋል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለ ጦር ነበልባል ብርጌድ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Jan, 09:17


አገዛዙ በከባድ መሳሪያ ድብደባ ጉዳት አድርሶበት የነበረው ከጣርማበር-ደሴ የሚዘረጋው የኤሌክትሪክ መስመርን እያስጠገነ እንደሚገኝ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃ ገለፀ።

የውድቀት ዋዜማ ላይ የሚገኘው የብልፅግና አገዛዝ የደግፉኝ ተሰለፉልኝ ሰልፍ ለማካሄድ በተለያዩ የአማራ ከተሞች ሊያሳካው ያቀደው ፕሮፖጋንዳ ሲከሽፍበት የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ነፃ ባወጣቸው እና በተቆጣጠራቸው ቀጠናዎች ደግሞ የአገዛዙን ፕሮፖጋንዳ ያከሸፉ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች መካሄዳቸው ይታወቃል።

በዚህ ድርጊት የተበሳጨው እና ከሕዝብ ልብ ውስጥ ጨርሶ የወጣው የብልፅግና አገዛዝ የተቃውሞ ሰልፍ በተደረገባቸው ሁሉም አካባቢዎች ከፍተኛ የሠራዊት ክምችቱን ከያለበት አሰባስቦ ጦርነት ቢከፍትም በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ሁሉም ክፍለጦሮች በተወሰደበት የተቀናጀ እርምጃ ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዶል።

በተለይ ባለፉት 6 ቀናት በሸዋሮቢት ዙሪያ ራሳና ማፉድ ሰብሮ ለመግባት ሙከራ ያደረገው የአገዛዙ ኃይል በራምቦ ክፍለጦር እና አባት አርበኛ ኃይል በደፈጣና በመደበኛ አውደ ውጊያ  ተደምስሶ ሲበታተን የተቀረው ደፈጣ በያዘ ኃይል ተለቃቅሞ ሙትና ቁስለኛ ሆኗል። ከዚህ የተረፈውም እምቦራይ ተራራ፣ ደማም ጉባ እና ሳላይሽ መሽጎ ይዟል። በለስ ቀንቶት ከፋኖ ጥይት ተርፎ በየተራራው ላይ የመሸገውንም ተከቦ በውሃ ጥምና በችጋር እያለቀ እየተቀጣ ይገኛል።

በዚህ አውደ ውጊያ ሽንፈት የደረሰበት የብልፅግና ተላላኪ ቡድን ከሙትና ቁስለኛ የተረፈው ለብ ለብ ሰራዊት በመበሳጨቱ በርቀት የመድፍ ፣የሞርተርና የዙ-23 ተደጋጋሚ ድብደባ በመፈፀሙ ከጣርማበር እስከ ደሴ ከተማ የሚዘረጋውን ዋናውን የኤሌክትሪክ(መብራት) አገልግሎት መስመር ከ18/04/2017 ዓ.ም ጀምሮ ውድመት አድርሶበታል።

በዚህ መልኩ የማሕበራዊ አገልግሎት ሀብቶችን ፣የጤና ተቋማት ፣የትምርት ተቋማትና የንፁሃን ጭፍጨፋ ሀብትና ንብረት ውድመት የሚፈፅመው የአብይ አህመድ አገዛዝ በፈፀመው ውድመት የተቋረጠው የመብራት አገልግሎት ጥገና እንዲጀምር ተደርጓል።

የብልፅግና ሠራዊት ባደረሰው ውድመት ለተከታታይ 6 ቀናት ተቋርጦ የነበረውን የመብራት አገልግሎት ለማስጀመርና የማሕበረሰብ እንግልት ለመቀነስ ፤ ከጥገና ባለሙያዎች ጋር በመነጋገር ቀጠናውን ለባለሙያዎች ብቻ በመፍቀድ በቂ ጥበቃና ከለላ በመስጠት ከጣርማበር -ደሴ የተቋረጠውን አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ለማስጀመር የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ብርቱ ጥረት እያደረገ ይገኛል ብሏል።

ተቋማትን በማውደም፣ ተፈጥሯዊ ረሀብ በመፍጠርና ማህበራዊ አገልግሎቶችን በማቋረጥ የሕዝብን ትግል ማሸነፍ አይቻልም ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Jan, 08:03


የፍርድ ቤት የችሎት ውሎ!

ትላንት ማለትም 22/04/2017 በእነ ዶ/ር ወንዶሰን አሰፋ መዝገብ የተቀጠረው የተጨማሪ የምስክር መስማት ቀጠሮ ን በተመለከተ ችሎቱ ብይን ሰጥቷል ።

ችሎቱም በአቃቤ ህግ የተነሳውን ለማሰማት ከዘረዘርናቸው 96 ምስክሮች ውስጥ 25 አቅርበን አስመስክረናል ። ቀሪዎቹን 71 የዓቃቤ ህግ ምስክሮች ለማቅረብ አሁን አማራ ክልል ያለው የሰላም ሁኔታ ስላስቸገረን እና ደ/ብርሀን አካባቢ ያሉንን ማስረጃዎች ማቅረብ ስላልቻልን ተጨማሪ ቀጠሮ ይሰጠን በማለት ጠይቋል ።በተከሳሽ ጠበቆች በኩል ደግሞ አቃቤ ህግ በቂ ግዜ ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም ብሎ የአገዛዙን ፍላጎት ለማሳካትና እኛን በግፍ ለማሰቃየት እየሰራ ይገኛል ። ከተሰጠው 9 የምስክር መሠማት ቀናት ውስጥ 6 ቀናትን ብቻ ለዚያውም ለ1 ሰአት የማይሞላ ጊዜ ምስክር አቀረብሁ በማለት ሲያስመስልና ሲያሾፍብን ነው የቆየው ። ይህ ቢሆንም የመጨረሻ ተብሎ አንድ አጭር ቀጠሮ ይሰጠው በማለት ተከራክረው በእለቱ ማለትም አርብ 18/04/2017 ሁለት ዳኞች ብቻ በመሠየማቸው ይህን አይነት መብት የሚያሳጣ ውሳኔ በ3 ዳኛ እንዲወሰን ደንቡ ስለሚያዝ ችሎቱ ቀጠሮ ለመሥጠት ለዛሬ አድሯል።

በመሆኑም ችሎቱ የቀረበውን ክርክር ተመልክቶ ተጨማሪ ቀጠሮ ለምስክር መስማት መሠጠት አለበት በማለት በይኗል ።

የቀጣይ የምስክር መስሚያ ጊዜ ከየካቲት 10_18/06/2017 ዓ.ም ቀጥሯል። በዚህ ጊዜ በብይኑ ላይ ተከሳሾች ከፍተኛ ቅሬታ በችሎቱ ላይ አቅርበዋል።

ቅሬታ ካቀረቡት መካከል
1ኛ * አቶ አለልኝ ምህረቱ (የታሰረ ጠበቃ) ቅሬታውን ሲያቀርብም "ፍርድ ቤቱ የእኛን ክርክር አልመዘነልንም ። ምክንያቱምያቀረብነውን ክርክር ከግምት ብታስገቡልን ኖሮ ይህ ብይን ለኛ አይገባንም ነበረ "በማለት ቅሬታቸውን ሲያቀርቡ

2ኛ* ቅሬታውን የገለፀው ዶር ሲሳይ አውግቸው ነው ። እንዲህ አለ "ቀጠሮ ይሰጠው ።ነገር ግን አጭርና የመጨረሻ መሆኑ ለዓቃቤ ህግ ይገለፅለት" ብለዋል።

3ኛ ቅሬታውን በምሬት ያነሳው አርቲስት ዮርዳኖስ አለሜ (ያበጠው ይፈንዳ ) ነው ። አርቲስቱ ሲናገር እኛ በችሎቱ እየተሰቃየን ያለነው ተከሳሾች በማይመለከቱን 3 ጉዳዮች ነው ። የመጀመሪያው መዝገብ መብዛት ነው ። አዎ በዝቶባችኋል ። ነገር ግን የመዝገብ መብዛት እኛን የሚመለከት ጉዳይ አይደለም ። አንድ የሽብር ችሎት ምን ያክል መዝገብ መያዝ አለበት ? አንድ የሽብር መዝገብስ በምን ያክል ጊዜስ የተፋጠነ ፍትህ ማግኘት አለበት የሚሉትን ጥያቄዎች እራሳችሁ ዳኞችና ተቋሙ መመለስ ያለባችሁ ጥያቄዎች ናቸው ። 7 መዝገብ ብቻ መያዝ እያለባችሁ 56 ንፁሀነሰ የአማራን ተወላጆችን መዝገብ ለእንጀራችሁ ስትሉ ሰብስባችሁ ይዛችሁ የናንተ ልጆች እንጀራ ሲበሉ የኛ ልጆች ጎዳና እየወጡ መሆኑን አታውቁም ? ሁለተኛ የተፋጠነ ፍትህ ሳላገኝ ዛሬ ሁለት አመታትን በግፍ ታስሬአለሁ ። ተደብድቤአለሁ ። አካሌን አጉድሎታል ይህ ግፈኛ አገዛዝ ። ቤተሰቦቼ ተበትነዋል። ልጆቼ ትምህርታቸውን አቋርጠዋል። የሚበሉት የላቸውም። በዚህ ላይ ገና ይህ 71 ምስክር ማቅረብ አልችልም እያለ አቃቤ ህግ ሁለት አመታት ተጨማሪ ቢያቆየኝ ከ4 አመት እስር እንግልት ስቃይ መከራ ከተፈራረቁብኝና ቤተሰብ አልባ ከሆንኩ ቡሀላ ነፃ ብላችሁ ብትፈቱኝ እኔ ምንም የማልሰራ ሙሉ አካሌ በአካልም በስነልቦናም በኢኮኖሚም የደቀቀ ተጧሪ እንደምሆን አታውቁም ????ይህ ፋሽስት ስርአት እኔን እንደዚህ እንዲያደርገኝ ደግሞ መሳሪያ አድርጎ የተጠቀማችሁ ይህን ችሎትና ፍርድ ቤቱን ነው። ይሄንንስ አስተውላችሁታል ???
በመጨረሻም ዓቃቤ ህግ የሚያስመሠክረው ምስክር ስለሌለው እንጂ ጠቅላይ ተብየው ኢትዮጵያ ሰላሟን አረጋግጣ በብልፅግና ጉዞ ላይ መሆኗን መግለጫ በሰጡበት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ኢትዮጵያ ከእንግሊዝ በላይ ሰላሟ የበለጠ የተረጋገጠ ሆኗል ባሉበት ተመስገን ጥሩነህ አማራ ክልልን 100%ተቆጣጥረን እየመራን ነው ባሉበት አማራ ክልል ሰላም ስለሌለ ብሎ ምክንያት መደርደር በችሎቱ ተቀባይነት ሊኖረው አይገባም በማለት ቅሬታውን እንባ እየተናነቀው አቅርቧል።

በተጨማሪም በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በቅጣት ቤት ውስጥ ከእነ የተከበሩ ዮሀንስ ቧያለው ጋር ስለሚኖር ለጤንነቱና ለጋራ አኗኗራቸው ያልተመቻቸውን ሁኔታዎች በመግለፅ በፅሁፍ ማመልከቻ ለችሎቱ አቅርቧል።

ዳኞችም የቀረበውን አቤቱታ ካዳመጡ ቡሀላ በችሎት የማይነገር የእናንተን መዝገብ አስመልክተን ያደረግነውን ጥረት እንንገራችሁ አሉና እኛ ስራችን በችሎት የቀረበልልን ምስክር መስማት ብቻ ነው ግዴታችን። ነገር ግን በማይመለከተን ጉዳይ ጭምር የከፍተኛ ፍርድ ቤት ከፍተኛ አመራሮች ጋር ሁላችንም የዚህ ችሎት ዳኞች ገብተን ዓቃቤ ህግ በተቻለ መጠን በተያዘው ጊዜ ውስጥ በትጋት ምስክሮችን እንዲያቀርብ ከፍትህ ሚንስቴር ጋር እንዲነጋገሩ ጠይቀናል። ይህ ሙከራ ከእናንተ መከራና መንገላታት አንፃር በቂ ባይሆንም ዝም ግን አላልንም ። ያለብንንም መከራ ተረዱን እኛም አልተመቸንም ስቃይ ውስጥ ነን ብለዋል።

ተጨማሪ ችሎት ይሰየምና መዝገቦች የተፋጠነ ፍትህ እንዲያገኙ አድርጉልን ብለው አርቲስት ዮርዳኖስ አለሜ ያነሱት ትክክል ቢሆንም ዳኞች በከፍተኛ ሁኔታ ስራ እየለቀቁ በመሆኑና አዳዲስ የዳኞች ሹመት ለሁለት አመታት ስላልተሾመ የሚቻል አይደለም በማለት ዳኞቹ ተናግረዋል ። በመጨረሻም ቀጠሮውን ማሻሻል አንችልም ቀጠሮው የካቲት 10_10/2017 ተቀጥሯል።

በተጨማሪም ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ሁለት ወራት ለሚጠጋ ጊዜ ፍርድ ቤት ስለማንመጣ በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የደረሰብንን ችግር እንናገር በማለት ተናግሮ ረ/ኢ/ር መስፍን ግርማ የጥበቃ ሀላፊ ቤተሰቦቻችን ምግብ ሲያመጡ ክብራቸውን በሚያሳጣ ሁኔታ ፍተሻ በማለት አማራ ጠል መሆኑን እያሳየና ጠያቂ እያሳጣን ይገኛል እና ትዕዛዝ ይሰጥልን ብሏል።

ዳኞችም በቃል የቀረበው የጋዜጠኛ ጎበዜ አቤቱታ በፅሁፍ ይቅረብ በማለት ችሎቱ ተጠናቋል።

ውድ አማራውያን እነዚህ ንፁሀን የአማራ ተወላጅ የህሊና እስረኞች ፋኖ በበረሀ የአብይን ሰራዊት አከርካሬ እንደሰበሩትና አጭደው እንደከመሩት ሁሉ እነሱም የጨፍጫፊውን ፋሽስት አገዛዝ በራሱ አሻንጉሊት ፍርድ ቤት ውስጥ ፊት ለፊት ገጥመው እያፈራረሱትና መሣቂያ እያደረጉት ነው።

Ethio 251 Media

01 Jan, 07:43


ሰበር ዜና!

ሌ/ኮ ተካ መከቦ ጨምሮ በርካታ የጠላት ኃይል ተደመሰሰ ተደመሰሰ!

የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 48ኛ ክፍለጦር ከፍተኛ አዛዥ ሌ/ኮሎኔል ተካ መከቦ መሃመድን ጨምሮ በመቶዎች የሞቱበትና የቆሰሉበት ታላቅ ድል ራያ ቆቦ ዞብል ላይ ተፈፀመ::

የአማራ ፋኖ በወሎ ምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለጦር ራያ ቆቦ ዞብል ከተማ እና ዙሪያዉን ሰፍሮ የሚገኘው 48ኛ ክፍለጦር የጠላት ሃይል ትናትና ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም 10:00 ጀምሮ እስከ ሌሊት 7:00 ድረስ ከባድ ዉጊያ በመክፈት የክፍለጦር ከፍተኛ አዛዡን ኮሎኔል ተካ መከቦ መሃመድን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ የተደመሰሱበትና የቆሰሉበት ታላቅ ድል መስራታቸውን የአማራ ፋኖ በወሎ የምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሀብተማርያም መንበሩ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

መስከረምና ጥቅምት ላይ ራያ ቆቦ ተኩለሽና ዞብል በበርካታ ሰራዊትና መካናይዝድ እንዲሁም ድሮን ታግዞ የገባ ቢሆንም በተደጋጋሚ አሰልች የደፈጣ ጥቃቶችና ተጋድሎዎች በቅርቡ ተኩለሽን ያስለቀቅን መሆናችን የሚታወቅ ሲሆን ራያ ቆቦ ዞብልና አካባቢው ላይ የመሸገዉን 48ኛ ክፍለጦር ዞብል አምባ ክፍለጦር በበርካታ የደፈጣ ጥቃቶች በማሰላቸትና መፈናፈኛ በማሳጣት ከትናትና ጀምሮ እስከ ዛሬ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም በቀጠለው ዉጊያ በርካታ ድሎችን ተጎናፅፈዋል::

ዞብል አምባ ክፍለጦር በተጋድሎው

ከቡድን መሳሪያ አንድ ስናይፐር
ከነፍስ ወከፍ 7 ክላሽ፣ ተተኳሽ 2ሺ የክላሽ ጥሬ ገንዘብ 20000 (ሃያ ሺ ብር) ሬድዮ መገናኛዎችን ጨምሮ ጠላት የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት የሚፈፅምባቸውና የሚጠቀምባቸው ሰነዶችን መማረካቸውን የአማራ ፋኖ በወሎ የምስራቅ አማራ ኮር 2 ዞብል አምባ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሀብተማርያም መንበሩ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Dec, 18:10


🔥🔥ጎንደር የገባው ወራሪ ሠራዊት በየቀጠናው እየነደደ ነዉ🔥🔥

👉በሁሉም የጎንደር ቀጠናዎች ጠላትን የመቅበር ውጊያዎች ተቀጣጥለው ቀጥለዋል።

👉በዚህ መሠረት የመጀመሪያው መረጃችን ደቡባዊ ጎንደር በእስቴና በስማዳ መካከል ላይ የምትገኘው ሸንበቆች ላይ ሁለተኛ ቀኑን የያዘ ከፍተኛ ውጊያ እየተደረገ ይገኛል። የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ እስቴ ዴንሳ ብርጌድ፣ ሃገረ ቢዘን ብርጌድ እንዲሁም የሜ/ጄ ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክ/ጦሮች አማካኝነት በከፍተኛ ደረጃ ተመትቷል። ወራሪ ሠራዊቱ ከስማዳ፣ ከጠዶዬ፣ ከምክሬ ከእስቴና ከአንዳቤት ዛሬ ላይ ደግሞ ከወረታ ዋንዛዬን አቋርጦ፣ ከደብረ ታቦር እና ከክምር ድንጋይ የተንቀሳቀሰን ከፍተኛ ቁጥር ያለውን ኃይል አንቀሳቅሶ የነበረ ቢሆንም ያሰበው ሳይሳከ እንደቅጠል ረግፎ ሙትና ቁስለኛውን እየጎተተ ወደኋላ ፈርጥጧል።

👉ከዚህ ሌላ የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ ጥቁር አንበሳ ብርጌድ እና የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ፣ ነብዩ አሳምነው ከአዲስ ዘመን በወይንዬ አድርጎ ሚካኤል ደብር ለመግባት የተንቀሳቀሰን ወራሪ ሠራዊት ሲረፈርፉት ውለዋል። በዚህ አስደናቂ እና መብረቅ ክ/ጦር ቅንጅታዊ ኦፕሬሽንም ከአንድ ሻንበል በላይ የአገዛዙ ጦር እስከወዲያኛው ሲሸኙ ከ50 በላይ የነፍስ ወከፍ መሣሪያን፣ 30 የአገዛዙ ጦር እጅ ወደላይ ብሎ ገቢ ሆኗል።

👉ሁለተኛውና እጅግ አስደናቂው መረጃ ወደ 6ኛ ቀኑን የያዘው ከደባርቅ እስከ አምባጊዮርጊስ ያካለለውና በርካታው ወራሪ ሠራዊት እጁን የሰጠበት፣ እስከ ወዲያኛው የተሸኘበት፣ በመቶዎች የሚቆጠሩ የቡድንና የነፍስ ወከፍ መሣሪያዎች እየተገኘበት ያለው ውጊያ ነው።

👉በዛሬው እለትም አጅሬ አካባቢ በአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ እና በአማራ ፋኖ በጎንደር ቅንጅታዊ ምት ፤ከሞት የተረፈው ወደ እንቃሽ ተሻግሮ፣ የአምባ ጊዮርጊሱም የሙት ቅራውቹን ለመቀበል ተስቦ መጥቶ የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ ራስ ደጀን ክ/ጦር ነበልባሎች በሚያውቁት የማጫወቻ ሜዳ ላይ ከታችም ከላይም ስበውና ሰብስበው ሲወቁት ውለዋል። በጠዋቱ በተጀመረው በዚህ ዓውደ ውጊያ በርካታ የአገዛዙ ሠራዊት እንደቅጠል ረግፏል።

👉ከዚህ በተጨማሪም በዳባቱ አቅጣጫ ኃይል ለመክፈል ከወቅንና ከዳባት አቅጣጫ የተንቀሳቀሰን ኃይል የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ አያሌው ብሩ ክ/ጦር አረቡር፣ ጭላና በንከር እንደ እንደቅጠል ሲያራግፉት ውለዋል።

👉ሦስተኛው መረጃ የሻሁራውን ተጋድሎ ይመለከታል። ከትናንት ጀምሮ ከፍተኛ ትንቅንቅ እየተደረገበት ባለው በዚህ ዓውደ ውጊያም የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ አድዋ ክ/ጦር፣ ንጋት ጮራ ብርጌድ ጠላትን ከፍንጀት አፋፍ ላይ ወደ ታች ወደ ወኩ ስልታዊ ማፈግፈግ አድርገው ጎትተው ገደል ስር አስገብተው በከፍተኛ ደረጃ መትተውታል።

👉አራተኛው የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ ድል በር ብርጌድ ከማክሰኝት ወደ ጄራ ሚካኤል የተንቀሳቀሰን የአገዛዙ ወራሪ ሠራዊ መንገድ ላይ ገዥ ቦታዎችን በመያዝ 4 ቦታዎች ላይ አስደናቂ ደፈጣ በመጣል በርካታውን ሙትና ቁስለኛ አድርገው ወደ ማክሰኝት ከተማ ፈርጥጦ እንዲገባ ተደርጓል።

👉በመጨረሻም ምዕራብ ጎንደር ዞን፣ አርባ ጅርሃ ወረዳ፣ ሞገሴ ከተማ ላይ የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ አጣናው ዋሴ ክ/ጦር እና የአማራ ፋኖ ጎንደር እዝ፦ ጎቤ ክ/ጦር በተውጣጡ ኃይሎች በርካታ ሚሊሻና አድማ ብተና ባንዳዎች ተቀንድሸዋል።

👉በጥቅሉ ጠላት ያቀደው የኅልውና ታጋዮን እየነጠለ ከፍተኛ ቁጥር ባለው ሠራዊት ለመምታት፣ ፋኖን በትኘዋለሁ የሚል የበትኘዋለሁ ፕሮፓጋንዳ የመሥራት ፍላጎቱን ያፈረስንባቸው፣ ከፍተኛ የትጥቅ ቁሳቁሶችን የታጠቅንባቸው፣ በወራሪ ሠራዊቱ ላይ የውጊያ የበላይነትን የወሰድንባቸው፣ የሥነ ልቡና ስብራትን ያደረስንባቸው የድል የአሸናፊነት ውጊያዎች አድርገናል፤ እለታዊ እቅዳችንንም ከበቂ በላይ አሳክተናል ሲል የአማራ ፋኖ በጎንደር የሚዲያና ሕ/ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Dec, 17:04


ሰበር ዜና!

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አራተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የራሳው አውደውጊያ ቀጥሏል!!

ጥላት የብልፅግና ጦር በራሳ ፋኖን ፀጉሩን እየያዝን ከጎሪያቸው መዘን እናወጣቸዋለን ያለው የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ሰራዊት መውጫ ጠፍቶበት በለስ የቀናው እጁን ሲሰጥ የተቀረው አስከሬኑን ቀባሪ አቶ ጅብ እየጮኸበት ይገኛል።

አራተኛ ቀኑን ያስቆጠረው የራሳው ተጋድሎ በፋኖ ለማ አስማማው ተወሪዋሪ የዕዙ ሻለቃ ልጆችና በራንቦ ክፍለጦር ድባቅ የተመታው የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ሰራዊት ከደብረብርሃን ተጨማሪ ሀይል በማስጠጋት ዙ -23 ታጥቆ ያንቀሳቀሰ ቢሆንም ጉዶበረት ላይ የአስቻለው ደሴ ክፍለጦር በደፈጣ እያረገፈችው ትገኛለች ።

በተጨማሪ ከደብረሲና እስከ ሸዋሮቢት መግቢያ በሸዋ ጀግኖች መንገዶች ሁሉ ዝግ የተደረጉ ሲሆን በሾላሜዳ ፣አርማኒያ ፣ጭራሜዳና አስፋቸው በጀግኖቹ ደፈጣ ተጠርቅሞ ተይዟል
ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 10:26


በአገዛዙ ሠራዊት በወልድያ በግፍ የተገደለው ወጣት ሚፍታህ አሚኑ አዛኝ ታሪክ!

ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 10:16


የአማራ ፋኖ በጎጃም የተፈራ ዳምጤ ክፍለጦር የደጋ ዳሞት ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ዳሞት አለኸኝ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 10:04


የአማራ ፋኖ በጎጃም 1ኛ ክፍለጦር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሙሉሰው የኔአባት ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 09:59


የአማራ ፋኖ በጎጃም የ3ተኛ ክፍለጦር አቤ ጉበኛ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አብርሃም ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 09:51


የአማራ ፋኖ በጎጃም የኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ መራዊ ከተማን መቆጣጠሩ ተሰምቷል።

38 የአገዛዙ ሰራዊት ሲደመሰስ 12 ተማርኳል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም አንደኛ ክፍለጦር ነኮሎኔል ታደሰ ሙሉነህ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሔኖክ አሸብር ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 09:28


ሰበር ዜና!

17 ሙትና 29 ቁስለኛ ሁኗል፤ አሁንም በከበባ ውስጥ ይገኛል!

የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ላስታ አሳምነው ኮር ተከዜ ክፍለጦር እና ጥራሪ ክፍለጦር በጋራ ባደረጉት ተጋድሎ ታላቅ ድል ተጎናፅፈዋል::

ላስታ አሳምነው ኮር ከተቆጣጠራቸው አካባቢዎች አንዱ በሆነው ኩልመስክ ቀጠና ለማጥቃት ሶስት ሬጅመንት ከመካናይዝድ ጋር ያሰለፈው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት በፋኖ ኮማንዶ ዘላለም ሲሳይ የሚመራው ተከዜ ክፍለጦርና በአርበኛ ሻለቃ ብርሃን አሰፋ የሚመራው ጥራሪ ክፍለጦር ባደረጉት ብርቱ ትንቅንቅና ተጋድሎ በርካታ ሙትና ቁስለኛዉን ይዞ የተመለሰ ሲሆን ጠላት አሁንም ኩልመስክ ላይ ተከቦ ይገኛል::

ከራያ ቆቦ ተኩለሽና አካባቢው በበርካታ ተደጋጋሚ የደፈጣ ጥቃት ተሰላችቶና መፈናፈኛ አጥቶ ወደ ጊዳን ወረዳና ኩልመስክ የገባው ጠላት ቀጠናዉን ከአመት በላይ ተቆጣጥረው በሚገኙት የላስታ አሳምነው ኮር አሃዶች ጥራሪ ክፍለጦርና ተከዜ ክፍለጦር ተቀብለው እያስተናገዱት ይገኛሉ::

ኩልመስክና ሃሙሲት አካባቢ በተደረገው ጠንካራ ዉጊያ የጠላት ሰራዊት የተረፈረፈ ሲሆን 17 ሙትና 29 ቁስለኛ ሁኗል፤ ቀሪው የጠላት ኃይልም ኩልመስክ ላይ ከበባ ውስጥ ገብቶ እጅ ስጥ እየተባለ ይገኛል፤ ተጋድሎው ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም ንጋት ጀምሮ እስከ ምሽት 1:00 ድረስ በጀግኖቹ ተከዜ ክፍለጦር እና ጥራሪ ክፍለጦር ትንቅንቅ የቀጠለ ሲሆን አሁንም የገባው ጠላት በማይወጣበት ሁኔታ ተከቦ ይገኛል::

ቅዱስ ላሊበላ ከተማና ቀጠናው ላይ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ድል ለማግኘት የቋመጠው የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ጦር በተለያየ አቅጣጫ ወደ ቅዱስ ላሊበላ ከተማ ሬሽን ለማስገባት ቢሞክርም የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት በመጣበት አቅጣጫ ሁሉ እንደ እባብ እየተቀጠቀጠና እየተደመሰሰ ይገኛል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 09:27


የአማራ ፋኖ በጎንደር ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሀቅአለው ፀጋ አለባቸው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተተተሉት......

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 09:24


የብልፅግናው ቡድን ከቀን ወደ ቀን መፈራረሱ ቀጥሏል።

በዚህ ሁለት ቀን ብቻ በርካታ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት አመራሮ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝን ተቀላቅለዋል።

በትናንትናው እለት ከምንጃር ሸንኮራ ወረዳ 1 በመቶ አለቃ ማዕረግ ያለው ሻንበል መሪ 1 በሃምሳለቃ ማዕረግ ያለ ም/ሻንበል መሪ የሰራዊት አባላትን እና ሚሊሻዎችን በመያዝ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ነበልባል ብርጌድን ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የተቀላቀሉ ሲሆን አንድ የመከላከያ አባል አንድ እስናይፐር እና ሁለት ክላሽእንኮቭ በመያዝ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ተስፋ ገብረስላሴ ብርጌድን የተቀላቀለ ሲሆን 1እስናይፐርና አንድ ክላሽ አኮቭ በመያዝ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ፊትአውራሪ አስማረ ዳኜ ብርጌድን የተቀላቀሉ ሲሆን በሌላ መረጃም 2የሚሊሻ አባላት ከደብረብርሃን ከተማ ከሙሉ ትጥጥቃቸው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ነጎድጓድ ክፍለጦርን ተቀላቅለዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ 8የሚሊሻ አባለት ከእነዋሪ ከተማ በነሳት ከነሙሉ ትጥቃቸው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር ራስ አበበ አረጋይ ብርጌድን ተቀላቅለዋል።

ከሰሞኑ ከፍተኛ ተጋድሎ ሲያደርግ የሰነበተው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር እራስ አበበ አረጋይ ብርጌድ በጦር ሜዳ ያገኘውን ድል በፖለቲካው መድረክም ደግሞታል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 09:17


በዘመቻ ፊታውራሪ ደሳለው ስጦት እና ግራ አዝማች አረቡ ታደሰ ሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ቃኝ የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ላይ ከባድ እርምጃ በመዉሰድ ታላቅ ድል መጎናፀፋቸው ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ በወሎ የምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ዋና ቃል አቀባይ ፋኖ ቃልአብ ወርቅዬ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 09:04


ሰበር ዜና!

በትላንትናው ዕለት ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም አይበገሬዎቹ የጣና ገላውዴዎስ ረመጦች ከአርብ ገበያ በሁለት አቅጣጫ የመጣን ወራሪ ሠራዊት አሳሩን ሲያሳዩት ውለዋል።

በአርበኛ ማሩ ቢተው አጋፋሪነት የመጀመሪያው ቤላ አቦን ለመያዝ ለመያዝ መነሻውን አርብ ገበያን አድርጎ እንቅስቃሴ ቢያደርግም ቅስሙም ተሰብሮ እቅዱም ፈርሶ በመጣበት እግሩ ፈርጥጦ ተመልሷል።

ከረፋዱ 3:00 ሰዓት የጀመረው የዚህ ግንባር ዓውደ ውጊያ ልዩ ቦታው "አለቃ ጎራ" የተባለ ቦታ ላይ እስከ ምሽት 12:00 ሰዓት ድረስ ዘልቆ በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ለማድረስ ተችሏል። በዚህም መሠረት ከ80 በላይ የአገዛዙ ጦር እስከ ወዲያኛው ሲሸኝ፣ በርካታ ቁስለኛም የተመዘገበበት ነበር። ሁለተኛው ግንባር ከአርብ ገበያ ተነስቶ ወደ ሳና ከተማ የተንቀሳቀሰን ወራሪ ሠራዊትም በተመሳሳይ በጣና ገላውዴዎስ ነበልባሎች ተለብልቦ ተመልሷል።

በጥቅሉ የአርብ ገበያው አውደ ውጊያ ጠጅ መረር፣ ቅምጦ፣ ሳና ሚካኤል፣ መንታ ውሃ፣ ኪዳነ ምሕረትና ሌሎችም ጎጦች ላይ ሰፊ ዓውደ ውጊያ ተከናውኖ የአማራ ፋኖ በጎንደር ጣና ገላውዴዎስ ክ/ጦር ድንቅ ኦፕሬሽን በጠላት ላይ ሁሉን አቀፍ የበላይነትን መቀዳጀት ተችሏል።

በተመሳሳይ ትላንት ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም የአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክ/ጦር እስቴ ዴንሳ ብርጌድ እና አንዳቤት ብርጌድ በጠላት ላይ ድልን ተቀዳጅተዋል። ከእስቴ ከተማ በ3 ኪ.ሜ ርቀት ላይ በተደረገው ውጊያ የእስቴ ዴንሳ ብርጌድ ነበልባሎች የአገዛዙን ጥምር ጦር በወጉ ሲበልቱት ውለዋል።

የከተማው ፖሊስ አዛዥ ሳይቀር በመንገድ መሪነት በተሳተፈበት በዚህ ውጊያ አይበገሬዎቹ የፖሊስ አዛዡን አጃቢዎች፣ ከ30 በላይ ሚሊሻ፣ በርካታ ወራሪ ሠራዊቱን እስከወዲያኛው ሲሸኙ የወረዳው ም/ፖሊስ አዛዥና በውል ያልታወቁ ባንዳ አመራሮችም ክፉኛ ቆስለው በማጣጣር ላይ ይገኛሉ። ሌላኛው የአንዳቤት ብርጌድ ክንደ ነበልባሎችም አለም በር እና ቀጭን ሜዳ ላይ ጠላትን ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።

ሌላው የአማራ ፋኖ በጎንደር ዞዝ አምባ ንጉሥ ክ/ጦር፣ አግኝቸው ብርጌድ ከእብናት ተነስቶ የጀግናው አስቻለው ደሴ መካን የሆነችውን ሰላማያ ከተማን ለመያዝ ከፍተኛ ኃይል ጭኖ ቢንቀሳቀስም የአርበኛ ዮናስ አያልቅበት ልጆች ልዩ ቦታው አድራቆ ላይ በፈጸሙት ፋታ የማይሰጥ መብረቃዊ ጥቃት ወራሪውን ሠራዊት ብትንትኑን አውጥተው ወደ መጣበት መልሰውታል።

በመጨረሻም የአጼ ፋሲል ክ/ጦር እና አሳምነው ብርጌድ ለ2:00 ሰዓታት የቆየ ዓውደ ውጊያን አድርገው በርካታ የአገዛዙ ጥምር ጦር ከፍተኛ ኪሳራን አድርሰው ወጥተዋል። በሌላ በኩል የአሳምነው በርጌድ፦ ንሥር ሻለቃ አለም በር ከተማ ላይ አስደናቂ ኦፕሬሽን በመፈጸም በርካታ ሚሊሻን ደምስሳ በጀግንነት ወጥታለች ሲል የአማራ ፋኖ በጎንደር የሚዲያና ሕ/ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

28 Dec, 08:21


ሰበር ዜና!

በዘመቻ ፊታውራሪ ደሳለው ስጦት እና ግራ አዝማች አረቡ ታደሰ ሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ቃኝ የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ላይ ከባድ እርምጃ በመዉሰድ ታላቅ ድል ተጎናፀፉ::

የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር መቅደላ ክፍለጦር አካል የሆነው ሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ መቅደላ ወረዳ ልዩ ስሙ ድስም የሚባል ቦታ ላይ ከባድ የደፈጣ ጥቃት በመፈፀም ሶስት ባስ አንድ ፓትሮል የጠላት ሃይል ሙሉ ለሙሉ ደምስሰዋል:: በተጋድሎው የብልፅግና ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት አብዘሃኛው የጥይት ራት ሲሆን ቀሪው ገደል ገብቶ አልቋል::አንድ ፓትሮልም ከነ 12 ሰራዊቱ ሙሉ ለሙሉ ተቃጥሏል::

ሌላኛው የአማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር አካል የሆነው ታቦር ተራራ ብርጌድ ዘመቻ ፊታውራሪ ደሳለው ስጦትና ግራ አዝማች አረቡ ታደሰ በማስቀጠል አማራ ሳይንት ወረዳ ከባድ ትንቅንቅ ሲያደርግ የዋለ ሲሆን ጠላትን በርካታ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፅፏል::

በተጨማሪም ተንታ ወረዳ ላይ የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ የነበሩ አስራ አንድ ሚሊሾች ፋኖ ጋር አንዋጋም በማለት ትጥቅ ያስረከቡ ሲሆን አገዛዙ ሁሉንም አስሯቸዋል:: በቀጣይም ራሳቸዉን ከአገዛዙ ጥቃት ለመጠበቅም ሲባል ሚሊሾች ከነ ሙሉ ትጥቃቸው ፋኖን እንዲቀላቀሉ የፋኖ አመራሮችመልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል::

በቀጣይም መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ወሎ ቤተ-አምሐራ
ታህሳስ 18/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

27 Dec, 17:53


የዛሬ ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም “251 ዛሬ” ዝግጅታችንን በረንብልና በትዊተር ይከታተሉ ፡-
https://x.com/251Media/status/1872705725287616668

https://rumble.com/v63ehqe--december-27-2024-251-zare-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

27 Dec, 16:29


የአማራ ፋኖ በጎጃም ላለፉት አምስት ቀናት ለክፍለ ጦር አመራሮች የሰጠውን ስልጠና እና ያከናወነዉን ድርጅታዊ ግምገማ አጠናቀቀ::

የክፍለ ጦሮች አመራሮችን ጨምሮ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር በስራ አመራር፣ በአማራ የህልውና ተጋድሎ የትግል ስትራቴጅወች፣ በወታደራዊ የትጥቅ ትግል ስልቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ስልጠና ሰጥቷል።

ከስልጠናው መጠናቀቅ በኋላም የአማራ የህልውና ትግል ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ የሚመለከት መወያያ አጀንዳ ቀርቦ ሰፊ ክርክር እና ውይይት ተደርጎበታል::

በስልጠናው እና ድርጅታዊ ግምገማው ሂደት የአማራ ፋኖ አደረጃጀቶች የጋራ አመራር መፍጠር እና አንድ ድርጅት መውለድ ትንሹ ግዴታቸው መሆኑን አውቀው እንዲሰሩ እና ይህንንም የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር በትጋት እንዲያስፈፅም አስተያዬት ተሰጥቶበታል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም አመራር የውስጥ ግምገማ በመደበኛ ሁኔታ እንዲቀጥል እና የድርጅቱን ውስጣዊ የዲስፕሊን ጉዳይ በወታደራዊ ጨዋነት ህግጋት እና በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት ተፈፃሚ እንዲደረግም ሰፋ ያለ አስተያዬት ቀርቧል።

አዲስ ትውልድ!
አዲስ አስተሳሰብ!
አዲስ ተስፋ!
አስረስ ማረ ዳምጤ!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

27 Dec, 15:20


የአገዛዙ ሰራዊት አረመኔውን የብልፅግና  ስርዓት እየተወ ወደ አማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድን እየተቀላቀለ ይገኛል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ በትናንትናው ዕለት ማለትም በቀን 17/4/2017 ዓ.ም በምሽት 4:00 ሰዓት አካባቢ አረርቲ ሰርገው በመግባት የነበልባል ብርጌድ ጀብደኞቹ የሺ አለቃ አንድ ፋኖች አራዊቱ ሰራዊት የመሸገበት ምሽግ ላይ ጥቃት በመሰንዘር በጨበጣ ተኩስ ነበልባሎቹ የአገዛዙን ደንገጡር ሰራዊት ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።

ወደቀጠናቸውም በሰላም ተመልሰዋል።
አገዛዙም ሙትና ቁስለኛውን በፓትሮል እና በአንቡላስ አንስቶ ቁስለኛውን በአረርቲ መለስተኛ ሆስፒታል ያስገባ ሲሆን አንድ ከፍተኛ አመራርም ከፋኖ በተሰነዘረ ጥይት ተመቶ ቆስሎ በህክምና መትረፍ ሳይችል በነበልባሎቹ ጥይት እስከ ወዲያኛው ምድርን መሰናበቱን መረጃ ደርሶናል።

ይህንን የነበልባሎቹን ምት መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ሠራዊት ስርዓቱን አናገለግልም ከአማራ ህዝብ ጎን ተሠልፈን ይህን ያበቃለትን የአብይ ስርዓት እንገረስሰዋለን በማለት በዛሬው ዕለት በቀን 18/4/2017ዓ.ም በየአቅጣጫው የአገዛዙ ሰራዊት ፋኖን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።

አንድ መቶ አለቃ ሻንበል መሪ እና ምክትል ሻንበል መሪ ከነመገናኛ ሬድዮናቸው በጠዋቱ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድን በቁጥር ከ 9 በላይ ሚሊሻ እና 4 የመከላከያ ሰራዊት አባላት ፋኖ ወዳለበት የስርዓቱን አስከፊነት በውል ተረድተው እየተመሙ ይገኛሉ።

በዚህ የተደናገጠው የአገዛዙ ሠራዊት ወደ አራቱም የወረዳው ገጠራማ አካባቢዎች በማህበረሰቡ ላይ መድፍና ሞርተር በደመነፍስ እየተኮሰ የማህበረሰቡን ሠላምና ደህንነት እያናጋው ይገኛል።

በሞት መቃረቢያ ላይ ያለው የአብይ አህመድ ስርዓት እያበቃለት ይገኛል።

ድል ለአማራ ፋኖ !!!
ዘላለማዊ ክብር ስለትግሉ ሠማዕታት።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሠም ክ/ጦር ነበልባል ብርጌድ ፋኖ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል።

Ethio 251 Media

27 Dec, 14:19


ሰበር ዜና!

47 ሙትና ከ40 በላይ ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል!

ከሰሞኑ ሲቋጥር ሲፈታ፣ ሲጨነቅ ሲጠበብ፣ ሲሰበሰብ፣ ሲበተን። ሲሸክፍ ጓዝ ሲጠቀልል  የሰነበተዉ የጠላት ኃይል ዛሬ በሌሊቱ ከሰከላ፣ ከቲሊሊ፣ ከቡሬ እና ከማንኩሳ በአራቱ አቅጣጫ ተንቀራቅሶ ፋኖ ወዳለበት ቀጠና ጨለማን ተገን በማድረግ ቢያመራም የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ አገው ምድር ክፍለጦር ቲሊሊ ዘንገና ብርጌድን ለማፈን የሞከረዉ ከቲሊሊ የተነሳው ዘራፊ ቡድን መስከረም 29 ቀን መቶ አለቃ ማርቆስ ታምር በሰራበት ቦታ ላይ ከጠዋቱ 2:00 እንደደረሰ ቀድመዉ ቦታዉን ይዘዉት የነበሩት የቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ተርቦች 3ቱ ሻለቃ ከበዉ አፈር እያበሉት ባለበት ሰዓት ሌላኛዋ ሻለቃ ደግሞ በአርበኛ ዘመነ ካሴ ትዕዛዝ መሰረት ጠላት ወደ ጫካ ሲመጣ በቀጥታ ወደ ቲሊሊ ከተማ በመግባት በየፎቁ ላይ ተሰቅለዉ  የነበሩትን ለተከታታይ 3:00 ሰዓት በፈጀ ዉጊያ 5ቱ እስከ ወዲያኛዉ ሲሸኙ 11 ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ አገው ምድር ክፍለጦር ቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አለበል አወቀ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ይህ በእንዲህ በቀጠለበት ሰዓት ደን ስላሴ በተባለ ቦታ ላይ እየተለበለበ ያለዉን ኃይል የስሜነህ ደስታ እንጅባራ ብርጌድ ዕሮቡ ገበያ ሻለቃ እየበረረች ደርሳ በሽንጡ በመግባት በጠላት ላይ አረር አዉርዳበታለች ሲል ፋኖ አለበል አወቀ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተናግሯል።

በዚህ ግምባር  15 ሙትና ቁጥሩ ያልታወቀ ቁስለኛ አድርገዉታል። እንዲሁም
ከግዮን ሰከላ ብርጌድ የተወጣጡ ነበልባሎችም በፍጥነት በመድርስ ከዘንገና ብርጌድ ጋር ተጣምረዉ ለተከታታይ 5:00 ሰዓት በወሰደዉ ዉጊያ አሸባሪና ዘራፊ መንግስታዊ ቡድኑን 42 ሙት ሲያደርጉት ከ30  በላይ ቁስለኛም አሳቅፈዉታል።

በተመሳሳይ ከቡሬ ተነስቶ ወደ ደረቋ ያመራዉ ኃይል ደረቋ መግቢያ ላይ ረፍርፈዉ ወደ መጣበት እየለበለቡ ያስመለሱት ሲሆን ከወደ ማንኩሳና ሰከላ ከተማም ተንቀሳቅሶ የነበረዉንም ነበልባሎቹ የብረት አጥር በመሆን ካለበት እንዳይንቀሳቀስ ማድረግ ስለተቻለ፤ በአጠቃላይ ዘንገና ብርጌድና ስሜነህ ደስታ እንጅባራ ብርጌድ በነፃነት ባደረጉት ተጋድሎ በድምሩ 47 ሙትና ከ40 በላይ ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ አገው ምድር ክፍለጦር ቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አለበል አወቀ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል። በወገን በኩል 4 ቀላል ቁስለኛ ሲያጋጥም  አንድ የህይወትን መሳዉዕትነት መከፈሉንም አክሎ ገልጿል።

እንግዲህ ይህ ወንበዴ ቡድን በቀሩቱ አስር ቀናት ፋኖን አጠፋለሁ በሚል ቅዠት በሌሊቱ ሸክፎ ወደ ገጠራማዉ በመንቀሳቀስ ላይ ስለሆነ በአራቱም ክፍለ ሀገራት የሚገኙ ወንድሞቻችን ሁሌም ዝግጁ በመሆን እንደ አመጣጡ ማስተናገድ ያስፈልጋልና መዘናጋት እንዳይኖር አደራ ማለት እንወዳለን ሲልም የአማራ ፋኖ በጎጃም 3ተኛ አገው ምድር ክፍለጦር ቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አለበል አወቀ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

27 Dec, 10:32


የአማራ ፋኖ በጎንደር ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሃቅአለው ፀጋ አለባቸው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት .....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 20:26


የአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክፍለጦር እስቴ ዴንሳ ብርጌድ በአገዛዙ  ወንበር አስጠባቂ ሰራዊት አባላት ላይ በተመሳሳይ ሰአት በተለያዩ ግንባሮች ላይ በወሰደው መብረቃዊ ጥቃት ድል ተቀዳጀ።

የአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ሻለቃ ቢራራ እንደገለፁት  ዛሬ ሕዳር 28/2017 ዓ.ም ከቆማ ወደ እስቴ ሲጓዝ የነበረውን የአገዛዙን ወንበር አስጠባቂ ሰራዊት ገናመጫወቻ፣ ፅዮን፣ ሾለክት እና ሳጋ ላይ የማጥቃት እርምጃ በመውሰድ በርካታ የአገዛዙን ኃይል ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል። አንድ የጠላት ፓትሮልም ከጥቅም ውጪ ሆኗል።

ድል ለአማራ ሕዝብ
የአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክፍለጦር
ሕዳር 28/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

07 Dec, 17:23


የአማራ ፋኖ በጎጃም ህዳር 27/2017 ዓ.ም
የብርሸለቆ ምልምል ሰልጣኝ በፋኖ መበተኑ
===================================
ልማደኛው የ5ኛ(ራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም) ክፍለ ጦር ለ2ኛ ጊዜ ዛሬ የአብይ አህመድ ገዳይ ቡድን የሚፈለፈልበትን፣ የአማራውን ጭፍጨፋ የሚለማመዱበትን፣ስርቆት፣ነውረኝነት የሚሰበክበትን #ብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋምን በፋኖ እጅ ማስገባት ችለዋል።አንበሶቹ #የአረንዛው ዳሞት ብርጌድ፣#የደጃች አስቦ ቡሬ ዳሞት ብርጌድና #የክፍለ ጦሩ ጥምር ጦር በጥምረት ባደረጉት አውደ ውጊያ አማራውን ለመጨፍጨፍ ብርሸለቆ ወታደራዊ ስልጠና እየወሰዱ የነበሩት ምልምል ሰልጣኞች በርካቶች የፋኖን ጥይት ተግተዋል ሙትና ቁስለኛም ሁነዋል።
ከጥይት የተረፉትና እድል የረዳቸው ካምፑን ለቀው ወጥተዋል ተማርከዋልም።በተደረገው ውጊያ አሰልጣኝም ሰልጣኝም ተበትነዋል። ቁጥሩ ያልታወቀ ክላሸንኮቭ መሳሪያዎች ተማርኳል።
ፋኖ አሁን ላይ የተበተነውን የጠላት ኃይል እየሰበሰበ ይገኛል ከ2200 በላይ የሰልጣኝና አሰልጣኝ ገቢ ተደርጓል።

ጀብደኛው፣ ገጥሞ ሳይማርክ የማይመለሰውና ባለድሉ #የ3ኛ(ጎጃም አገው ምድር) ክፍለ ጦር ዛሬም እንደተለመደው የጠላትን ቅስም የሰበረ ወገንን ያኮራና ልብን ሞቅ የሚያደርግ ስራ ሰርተዋል።በአውደ ውጊያው የተሳተፉት አይደፈሬዎቹ ብርጌዶች
√የእንጅባራው #ቀኝ አዝማች ስሜነህ ደስታ ብርጌድ
√የዳንግላው #ቢትወደድ መንገሻ ጀንበሬ ብርጌድ
√የቲሊሊው #ዘንገና ብርጌዳ
√የሰከላው #ግዮን ብርጌድና
√የፋግታ ለኮማው #፲ አለቃ ኤፍሬም አጥናፉ ብርጌድ በጥምረት በዛሬው ዕለት መነሻውን ከኮሶበር፣ከቲሊሊ፣ከአዲስ ቅዳም፣ከዳንግላ በማድረግ ሰከላ ወረዳን ለመያዝ የተንቀሳቀሰው ጠላት በቲሊሊና በሰከላ ወረዳ መካከል በሚገኘኘው #ጉንድል ሰንሰለታማ ቦታ ላይ ሲቀጠቀጥ ውሏል።የጠላት 23ኛ ክፍለ ጦር፣73ኛ ክፍለ ጦርና 25ኛ ክፍለ ጦር በጥምረት ቢመጣም በፋኖ በኩል ደግሞ አንድ ክፍለ ጦር ብቻውን ጠላትን በመፋለም ሲደመስሰው ውሏል።የፋኖ አንድ ክፍለ ጦር የጠላትን 3 ክፍለ ጦር በመግጠም እልህ አስጨራሽ ትንቅንቅ ሲደረግ ውሏል።አንድ ለ3 በሆነ ratio ነው ውጊያው እየተደረገ ያለው።በዚህ አውደ ውጊያ ከፍተኛ የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛ ተደርግጓል።ጠላት ሲጠቀምበት የነበረው አንድ ኦራልና ሁለት ፓትሮል ተሽከርካሪ ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ ተደርጓል።
በአውደ ውጊያው የተማረከው
ከ30 በላይ የጠላት ኃይል ተማርኳል
አንድ ዲሽቃ
ሶስት ስናይፐር
ሁለት ብሬል(መትረጊስ)
ከ80 በላይ ክላሸንኮቭ መሳሪያ
አምስት አስቃጥላ የዲሽቃ ጥይት
አምስት አስቃጥላ የብሬል ጥይት
ቁጥሩ ያልታወቀ የክላሸ ተተኳሽና ሌሎች እንደቦንብ፣ትጥቅና መሰል ነገሮች መማረክ ተችሏል።

#የ1ኛ ክፍለ ጦር አካል የሆነው የይልማና ዴንሳው በጀግናው አርበኛ "ሻለቃ አንሙት ያዛቸው" ስም የተሰየመው ሻለቃ አንሙት ያዛቸው ብርጌድ በላይ ዘለቀ ሻለቃ ከአዴት ከተማ ወጥቶ ወደ ቋሪት አቅጣጫ እየተጓዘ በነበረው የጠላት ኃይል ላይ #በአዳማ ተራራ ላይ በከበባ ባደረገው ፍልሚያ 67 የአብይ ገዳይ ቡድን እስከወዲያኛው ሲሸኙ 49ኙ ደግሞ ከባድና ቀላል ቁስለኛ ተደርጓል።የሻለቃ አንሙት ያዛቸው ልጆች በደንጋ ሳይቀር ጠላትን ሲፋለሙት ውለዋል ድልንም ተጎናፅፈዋል።

የአብይ አህመድ ዘራፊ ቡድን በሰሜን አቸፈር ወረዳ ፎርሄ ኢየሱስ ቀበሌ፣አሲኗራ ሸሃንቲ ቀበሌ፣ቅላጅ ባርዳ ቀበሌ፣ሳንክራ ገነታ ቀበሌ፣... የነዋሪዎችን የተለያዩ ንብረቶች ላይ ስርቆት፣ውድመት አድርሰዋል።የአሲኗራ ሰሃንቲ ቀበሌ ነዋሪ ከሆኑ ግለሰቦች ከ600,0000 ብር በላይ ዘርፈዋል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!

ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ
የአማራ ፋኖ በጎጃም ምሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ምክትል ኃላፊ

Ethio 251 Media

07 Dec, 17:17


https://rumble.com/v5x03tk--251-zare-7-december-2024-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

07 Dec, 16:58


* የአፓርታይዱ አገዛዝ ሁሉን አቀፍ ጥቃት!

ኦህደድ መሩ ኦነጋዊው ብልፅግና እና ገረዱ ብአዴን መሩ ብልፅግና ሁሉን አቀፍ ጥቃት በአማራ ላይ እየፈፀመ ይገኛል። አማራን ከመሠረታት እና አጥንትና ደሙን፣ ህይዎቱን ከሰዋላት ሀገሩ አፈናቅሎታል። ኦነጋዊው እሳቤ ገና ከምስረታው ከትህነግ ጋር በመተባበር በአርባጉጉ፣ በበደኖ፣ በእንቁፍቱ፣ በአሰቦት እና በሌሎች አካባቢዎች ዘግናኝ የዘር ማፅዳት ጭፍጨፋ ፈፅሞበታል።

በኦህዲድ-ብልፅግና ዘመን በድጋሚ ኢትዮጵያ በእጁ የወደቀችለት የብልፅግናው ቡድን በስድስት ዓመታት ውስጥ አማራን ከኦሮሚያና ከአጎራባች ክልሎች ጭምር አፈናቅሎታል፣ ጨፍጭፎ በጅምላ እንዲቀበር አድርጎታል፣ ንብረቱን ዘርፎታል ቀሪውን በእሳት አውድሞታል፣ ቤተ እምነቱን አውድሞበታል፣ ከሩዋንዳዎቹ ቱሲ ከአይሁዳውያን የላቀ በሰው ልጅ የማይታሰብ አራዊታዊ ግፍ ፈፅሞበታል። ኦነጋዊው ቡድን ከብአዲናዊው ሎሌው ጋር በመተባበር በሁለቱም መስመሮች አማራ አዲስ አበባ (በራራ) እንዳይገባ ሰብአዊ የመንቀሳቀስ መብቱን ከልክሎታል።

የብልፅግናው ፊት አውራሪ በሆኑት በአብይ አህመድ እና በሽመልስ አብዲሳ ትዕዛዝ የሀገሪቱን ሀብት በማፍሰስ የጦር መሣሪያ በመግዛት ለአንድ ወር ያክል ከጅቡቲ ወደብ ወደ ኦሮሚያ በማጓጓዝ ያስታጠቀውን እና ሸኔ የሚል የቅፅል ስም የሰየመውን አጋንንታዊ ታጣቂ ከኦነጋዊው-ኦህዲድ ዓላማ አፈንጋጭ በማስመሰል ስምሪት በመስጠት በኦሮሚያ ክልል፣ በአማራ ክልል ኦሮሞ ብ/ዞን እና በአጎራባች ሰሜን ሸዋ ዞን በይፋት ቀጠና አማራ ላይ የዘር ማፅዳት ወንጀል ፈፅሟል። ከ2015 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ ደግሞ በመንግስታዊ ቁመናው በአማራ ላይ ጦርነት አውጆ የምድር፣ የአየር፣ የባህር ኃይሉን እና የክልል ኃይሎችን በማዝመት በሞርታር፣ በመድፍ፣ በታንክ እና በድሮን ንፁሃን አማራዎችን፣ ህፃናትና አረጋውያንን፣ የንፁሃንን ቤት እና እንስሳቶቹን ጭምር እየጨፈጨፈ ይገኛል። በዚህም ሁሉንም አይነት የጦር ወንጀል በግልፅ እየፈፀመ ይገኛል።

በዚህ ሁሉ አቅሙ አማራን አውድሞ ርስቱን ለመውረስ በሚያደርገው ትግል ፈፅሞ ያልገመተው አፀፋ በጀግናው ፋኖ እየቀመሰ የሚገኘው የአፓርታይዱ እሪያ ሠራዊት የድሃ አርሶ-አርብቶ አደር በሮቹን አርዶ እየበላ ይገኛል። ሰሞኑን በቤተ አምሓራ ወሎ ደቡብ ወሎ ዞን አምባሠል ወረዳ በሁለት ቀናት ብቻ 10 በሬዎችን አርዶ የበላ ሲሆን:-
1- የአቶ ይመር ከበደን ሁለት በሬዎች፣
2- የፋኖ ይመር ክበረት ሚስትን ሁለት በሬዎች፣
3- የአንዲት እንጨት በመሸጥ ኑሮዋን የምትገፋ እናት (እናኑ ብሬን) የግሏን አንድ በሬ እና የእኩል ያሣደገችውን ሌላ አንድ በሬ አርዶ በልቶባቸዋል። ይኸም አማራን በኢኮኖሚ የማውደም ሌላኛው የጥቃቱ መልክ ነው።

የሚያሳፍረው ደግሞ ይሄ እኩይ ተግባር የሚፈፀመው በሳይንት ተወላጁ ፻አለቃ ታደሰ በተባለ ባንዳ አስተባባሪነት ሲሆን የኩታበር ወረዳ ሚሊሻዎችም የዚሁ ድርጊት ተባባሪዎች ናቸው። የአምባሠል ውጫሌ አማራ በ2016 ዓ.ም. ፻አለቃ ሲሳይ በተባለ ባንዳ መሪነት በግፍ እየታሠረ ለዚሁ ባንዳ እስከ ፻ ሺህ ብር ድረስ ሲገብር ቆይቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ በአምባሠል ወረዳ በዛሬው ዕለት በቀን 28/03/2017 ዓ.ም. ቀበሌ 012 ስንዴ ምድር በሚባል መንደር ሻምበል ሞላ አማረ የተባለን ግለሰብ እና የዘመዶቹን ቤት በእሳት አቃጥሏል። ሻምበል ሞላ አማረ በትህነግ ወረራ ወቅት አምስት ጠላት ገድሎ በአማራ ክልል 'መንግስት' ሜዳሊያ የተሸለመ ጀግና ነበር። ዛሬ ግን ልጅህ ፋኖ ነው በማለት ኦነጋዊው አገዛዝ ቤቱን አቃጥሎበታል። ለዚህ ወንጀል የ'ወረዳው አስተዳዳሪ' በለጠ አራጋው እና አብዱ ጉማታው ተጠያቂ ናቸው። ፋኖም አብዝቶ ይበቀላል፤ ኦነጋዊው አፓርታይድ ስርዓት እስከ አፍቃሪ-አገልጋዮቹ በቅርብ ግብአተ መሬቱ ይፈፀማል። አርበኛ እና ባንዳ በአንድ እናት ጓዳ መኖሩ ያበቃል።

ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ህዳር 28/2017 ዓ.ም

Ethio 251 Media

07 Dec, 16:17


ሰበር ዜና!

ቋሊሳ ከተማ ሙሉ በሙሉ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገባች!

ለተከታታይ 15 ቀናት በሽምቅ፣ አልፎ አልፎም በመደበኛ ውጊያ መቆሚያ መቀመጫ አጥቶ የከረመው ወራሪ ሠራዊት ዛሬ ኅዳር 28/2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 8:00 ጀምሮ የገጠመውን መብረቃዊ የሽምቅ ጥቃት መቋቋም ሲሳነው ሙትና ቁስለኛውን በየመንገዱ እያንጠባጠበ በውድቅት ሌሊት ወደ እብናት ከተማ ፈርጥጦ ገብቷል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ ዞዝ አምባ ንጉሥ ክ/ጦር ረመጦችን ብርቱ ክንድ መቋቋም ሲሳነው ከተማዋ ላይ በቆየባቸው አጭር ቀናት የሕዝብን ጥሪት መዝረፍ፣ የአርሶ አደር ሰብል ማቃጠል፣ ለፋኖ ደጋፊ ናችሁ ብሂል የጅምላ እስር እና ድብደባ ፈጽም የማታ ማታ በአቅመቢስነቱ ተሸንፎ ከተማዋን ለቆ ወጥቷል ሲል የአማራ ፋኖ በጎንደር የሚዲያና ሕ/ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 14:48


ከአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቋራ ኦሜድላ ክፍለጦር ዋና አዛዥ ሻለቃ ሸጋ ጌታቸው የተሰጠ መግለጫ!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 10:34


በበለሳ ቀጠና በተደረገ ከፍተኛ ትንቅንቅ በርካታ ጀብዱዎች ተፈፅሟል።

በግንባር የተሸነፈው ነውረኛው የአገዛዙ ኃይል ህክምና ላይ የነበሩ ቁስለኞችን ከሆስፒታል አውጥቶ መረሸኑ ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የመብረቅ ክፍለጦር ዋና አዛዥ ኮማንዶ ያለው አዱኛ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 10:17


የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አመራሮች አውደ ውጊያ የተደረገባቸውን አካባቢዎችና በቀጠናው ላይ ያሉ የትግል ሒደቶችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ የአማራ ፋኖ በጎጃም ዋና ሰብሳቢ  አርበኛ ዘመነ ካሴ እና  ወታደራዊ አዛዡ አርበኛ ዝናቡ ልንገረህ ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ተገኝተዋል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 10:01


የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ የኔአለም ዘለቀ ከአማራ ፋኖ በጎጃም 5ተኛ ክፍለጦር የቋሪት ገረመው ወንድአወክ ብርጌድና ሻለቃ  አመራሮች በትግል ሂደትና ቀጣይ አቅጣጫ ዙሪያ ውይይትና ምክክር አድርገዋል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 09:43


የአገዛዙ ኃይል በንፁሃንና የሕዝብ መገልገያ ተቋማት ላይ የሃብትና ንብረት ውድመት መፈፀሙ ተገለፀ።

በውድመቱ የጤና ተቋማት ፣ የትምህርት ተቋማትና የግለሰብ መኖሪያ ቤቶች መውደማቸው ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የጎጃም አገው ምድር ክፍለጦር የቀኝ አዝማች ስሜነህ ደስታ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ዳግም ደሳለኝ ለኢትዮ ለኢትዮ 251 ሚዲያ መረጃ አድርሶናል።

ተከታተሉት ...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 09:35


በጎጃም ቀጠና በርካታ ተጋድሎዎች ሲደረጉ ከፍተኛ ድሎች ተመዝግበዋል።

በቀጠናው የተሰማራው የወራሪው ሠራዊት ክፍለጦሮች አከርካሪያቸው ሲመታ የተቀረው ሙትና ቁስለኛ መሆኑ ተገልጿል። 

የአማራ ፋኖ በጎጃም የበላይ ዘለቀ ክፍለጦር የዛምበረሃ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አባይነህ ምህረት ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 09:20


በወሎ ቀጠና ተጋድሎዎች አሁንም ቀጥለዋል።

የአማራ ፋኖ በወሎ የካላኮርማ ክፍለጦር ወልድያና ቆቦ ከተማ መካከል ዋና መስመር ላይ የምትገኘዉን ራያ ቆቦ ሮቢት ከተማ መቆጣጠሩ ታውቋል::

በተጋድሎው ዙፋን ጠባቂ ሰራዊቱም ሆነ ሆድ አደር ላይ ከባድ እርምጃ በመውሰድ በርካታው የተደመሰሰ ሲሆን በርካታ ቁስለኛ ወደ ወልድያ ሆስፒታል መወሰዱ ተገልጿል::

የአማራ ፋኖ በወሎ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት.......

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Dec, 09:04


በሸዋ ቀጠና በበርካታ አካባቢዎች በከፍተኛ ተጋድሎ ድል እየተመዘገበ ይገኛል።

በመለያ ዘመሮና ክምርድንጋይ ከፍተኛ ተጋድሎ በመፈፀም በጠላት ላይ ኪሳራ ሲደርስ በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ደጅዝማች ተሰማ እርገጤ ፣መሃመድ ቢሆነኝ እና ምኒልክ ክፍለ ጦሮች ውስጥ የተውጣጡ ሻለቃዎችና ብርጌዶች በጋራ ባደረጉት ተጋድሎ መንዝ/ሞላሌ ከተማን መቆጣጠራቸው ታውቋል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አበበ ሙላት ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

06 Dec, 19:30


ሰበር ዜና!

ለነጋሪ በሚከብድ ሁኔታ የአገዛዙ ወራሪ ሠራዊት እንደ ቅጠል የረገፈበት አውደ ውጊያ ተካሄደ። በደቡብ ጎንደር አርብ ገበያ ከተማ ላይ የመሸገውን አራዊት ሠራዊት የብረት አጥሮቹ የጣና ገላውዴዎስ ክ/ጦር ክንደ ነበልባሎች አሳሩን ሲያሳዩት ውለዋል።

የአርብ ገበያ ከተማን ሕዝብ ሰብስቤ አወያያለሁ በሚል እብሪት ያበደው የወረዳው ካድሬ ባንዳ እና የብርሐኑ ጁላ ሠራዊት ከጠዋቱ 2:30 ላይ ሕዝባዊ ውይይት በተቀመጡበት ሰዓት መብረቆቹ የጣና ገላውዴዎስ ክ/ጦር ረመጦች በሦስት አቅጣጫ ከተማዋን ወረራ በማድረግ የብልጽግና ወንበር አስጠባቂ ሠራዊትና ባንዳን እቅድም ቅስምም ብትንትኑን ሲያወጡት ውለዋል።

በአንደኛው አቅጣጫ የአንበሳው ብርጌድ፣ በሁለተኛው አቅጣጫ የአፈር ውሃእናት ብርጌድ እንዲሁም በሦሥተኛው አቅጣጫ የጣና ብርጌዶች በታቀደ ወታደራዊ ቅንጅት ከተማዋን የአስከሬንና የቁስለኛ ቃርሚያ ማሳ አድርገዋታል።

በዚህ አስደናቂ ኦፕሬሽን ከ3 ፓትሮል በላይ አስከሬን፣ 2 ፓትሮል ሙሉ ቁስለኛውን አሳቅፈውት ቅስሙንም እቅዱንም ሰብረው በጀግና ወግ እየተገማሸሩ ዓውደ ውጊያቸውን 8:30 አጠናቀው ወጥተዋል።

በዚህ መብረቃዊ ጥቃት ሳቢያ ቅስሙ የተሰበረበት የአገዛዙ ጦር ንጹሐንን በጅምላ ማሰር፣ ድብደባና ማሰቃየት የመሳሰሉ የሽብር ግብሩን አጠናክሮ ቀጥሎበታል ሲል የአማራ ፋኖ በጎንደር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ክፍል ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

Ethio 251 Media

06 Dec, 13:43


ሰበር ዜና

የአማራ ፋኖ ሸዋ  ዕዝ ከሰም ክፍለ ጦር ነበልባል ብርጌድ ዛሬ በቀን 27/3/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 በመሀል አረርቲ ከተማ በመግባት ጀብዱ ፈፅመዋል።

በሃምሳ አለቃ ፍቃዱ ጥላሁን ዋና ጦር አዛዥነት የሚመራው ግዙፉ የነበልባል ብርጌድ የሻለቃ ሁለት ተወርዋሪ ፋኖዎች መሀል አረርቲ ከተማ ሰርገው በመግባት የገዛ ወገኑን ከሚረሽነው የአብይ ምንጣፍ ጎታች ሰራዊት ጋር እንደ ቅርፊት ተለጥፈው በሚኒሻነት ሲያገለግል፣ ሴት ሲደፍር፣ አርሶ አደሩን በኬላ ሲደፍር እና ወጣቱን በማሳፈስ በግዳጅ ወደ መከላከያ ማሰልጠኛ ለመላክ ስምሪት ወስዶ ሲንቀሳቀስ የነበረው ሆድ አደሩ  ሚኒሻ ጠሃ ጀማል ቸርነት የታጠቀውን ክላሽ ከትከሻው ላይ አውርደው ግዳጃቸውን ፈፅመው ወደ ቦታቸው ተመልሰዋል ።

ብርጌዱ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃም እነዚህና መሰል ተግባራት ነጥለን በጥንቃቄ የምንፈፅማቸው ኦፕሬሽኖቻችን ማሳያዎች ናቸው ብሏል።

ብርሄዱ አሁንም በሚኒሻነት ሰልጥናችሁ ለተቀመጣችሁ ሞታችሁን ከመጠባበቅ ይልቅ አገዛዙን ትታችሁ ትጥቃችሁን በመያዝ ነበልባል ብርጌድን እንድትቀላቀሉ ሲል በጥብቅ አሳስቧል።

መረጃው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ነበልባል ብርጌድ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሀላፊ ፋኖ መ/ር አጥናፉ አባተ ነው።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

Ethio 251 Media

06 Dec, 13:22


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መንዝ ሞላሌ ከተማን ተቆጣጠረ።

የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ተጋድሎና ጀብዱ ሲቀጥል ዛሬም የመንዝን ሞላሌ ከተማን ተቆጣጥሮ ውሏል።

ከዛሬ ማለዳ ጀምሮ ሲፋለም የነበረው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለጦር እና ምኒልክ ክፍለጦር ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ ጠላትን በመረምረም ሞላሌ ከተማ ገብተዋል።  በከተማዋ ዙሪያ የቁም ምሽግ ቆፋሮ የነበረው የአገዛዙ ሀይልም ምሽጉ በንስሮቹ ተደርምሶ  ብዛት ያለው ሰራዊት ተደምድሷል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ገልጿል።

ዕዙ ታላላቅ ኮሮችን ካደራጀ በኋላ ከፍተኛ ተጋድሎዎችን እያደረገ ነው ያለው የዕዙ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ፋኖ ስንታየሁ ደመቀ ከሰሞኑ በተጠናከረ ሁኔታ የቀጠለው ተጋድሎ ከፍተኛ አመራሮች እየመሩና እየተሳተፉ እስከ መሀል ከተማም ዘልቀው እየገቡ የተዋደቁበት፣ የልዩ ኦፕሬሽኖቹን ዓላማም ለግብ ያበቁ ናቸው ብሏል።

ከሰሞኑ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ አምደፅዮን ኮር ራምቦ ብርጌድ እስከ ሸዋሮቢት ከተማ ገብቶ ድል ማድረጉ የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለት ደግሞ የደጃዝማች ተሰማ እርገጤ ክፍለጦር የመንዟን ሞላሌ ከተማ ተቆጣጥሯል።  ይህ ተጋድሎና ትንቅንቅም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ምክትል የህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ ፋኖ ስንታየሁ ደመቀ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

06 Dec, 13:08


''ከሰኞ ህዳር 30 ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ መንገዶች ዝግ ይደረጋሉ'' የአማራ ፋኖ በጎጃም።

የብልፅግና ወራሪ ሰራዊት በመደበኛ ጦርነት በህዝብ ላይ ከሚያደርሰው እልቂት ባሻገር በርካታ የውንብድና እና የሽብር ተግባራትን እየፈፀመ ይገኛል።

በከተሞች አካባቢ በየዕለቱ ወጣቶችን ይረሽናል፤ በየማጎሪያ ካምፖች ያጠራቅማል፤ ወደ ማሰልጠኛ ካምፖች ያግዛል። ከዚህ ጎንለጎንም የፋኖ ቤተሰቦችን ያስራል፤ ይረሽናል፤ ንብረት ያወድማል።

በማንኛውም ፀያፍ መንገድ የአብይ አህመድን ስልጣን ማስቀጠልን የመረጠው ወራሪ ሰራዊት ባንኮችን፣ ጤና ጣቢያወችን ዘርፏል፤ አውድሟል። በርካታ ትምህርት ቤቶችንም በመድፍ፣ በሮኬት፣ በድሮን እና በጀት አውድሟል። የገበያ ቀናትን እየመረጠ በሚያደርገው የወረራ ዘመቻ የማህበረሰባችንን ደህንነት ከባድ አደጋ ላይ ጥሌ ይገኛል።

ከሰሞኑም በሚተኩሳቸው መሳሪያወች በህዝብ ላይ ከባድ እልቂት እያስከተለ ይገኛል።
በመሆኑም ይህንን መሰል ጉዳቶችን ለመከላከል በምናደርገው ተጋድሎ ምክንያት የህዝብን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል ከመጭው ሰኞ ሕዳር 30/ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ግዜ:-

1) ከአምቡላንሶች በስተቀር መንገዶች ለሁሉም ተሽከርካሪወች ዝግ እንዲደረጉ መመሪያ ተሰጥቷል።

2) ለህዝብ ደህንነት ሲባል ከጤና ተቋማት በስተቀር ባንኮች፣ ትምህርት ቤቶች ጨምሮ የህዝብ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት ዝግ እንዲሆኑ ታዟል።

3) በመጨረሻም ሰራዊታችን እና መላው ህዝብ ወራሪውን ሰራዊት ለመመከት ለምናደርጋቸው ተከታታይ ወታደራዊ ጥሪወች በወትሮ ዝግጁነት እንዲጠብቅ እናሳስባለን

አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ትስፋ!
የአማራ ፋኖ በጎጃም!

Ethio 251 Media

30 Nov, 17:46


ፋኖ ተስፋማርያም ታፈሠ ስለ ኢትዮ 251 ሚዲያ…

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

https://www.ethio251media.org/be-a-member

Bank Acct Info: Chase Bank
Account number 675535275
Routing number 322271627

Zelle : [email protected]

Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

30 Nov, 16:20


https://www.youtube.com/live/k-B9cIU9AVo?si=2YXf314hn-CplEqs

Ethio 251 Media

30 Nov, 15:46


https://www.youtube.com/live/8w1QVOs1Uf0?si=JbkOr-9udtH4tSC1

Ethio 251 Media

30 Nov, 15:39


https://www.youtube.com/live/8w1QVOs1Uf0?feature=shared

Ethio 251 Media

30 Nov, 15:22


አርበኛ ዘመነ ካሴ ስለ ኢትዮ 251 ሚዲያ…

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

https://www.ethio251media.org/be-a-member

Bank Acct Info: Chase Bank
Account number 675535275
Routing number 322271627
Zelle : [email protected]
Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

30 Nov, 14:54


አርበኛ መከታው ማሞ ስለ ኢትዮ 251 ሚዲየ...

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

https://www.ethio251media.org/be-a-member

Bank Acct Info: Chase Bank
Account number 675535275
Routing number 322271627
Zelle : [email protected]
Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

30 Nov, 13:45


አርበኛ ሀብቴ ወልዴ ስለ ኢትዮ 251 ሚዲያ…

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

https://www.ethio251media.org/be-a-member

Bank Acct Info: Chase Bank
Account number 675535275
Routing number 322271627
Zelle : [email protected]
Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

30 Nov, 09:53


የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤቱ ቀደም ሲል ጠቅላይ ፍ/ቤት ከሰጠው ከታህሳስ 28/2017 ጊዜ ቀጠሮ ያጠረ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው የጠየቁ ቢሆንም ጠበቆች አቤቱታቸውን ለጠ/ፍ/ቤቱ አቅርበው የሚቀየር ነገር ካለ ጉዳዩን ሰብረው ለመመልከት ፈቃደኛ መሆናቸውን በማሳወቅ የጠ/ፍ/ቤቱን ውሳኔ ለመጠባበቅ ለጥር 13/2017 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተዋል።

2) አስማረ ወረቀት፦

ተከሳሹ ከቂሊንጦ ማ/ቤት በችሎት ተገኝቷል። በእለቱም በፌ/ከ/ፍ/ቤት በግራ ቀኙ የተደረገውን የሰነድ ክርክርን መርምሮ  ብይን ለመስጠት በሚል ለህዳር 24/2017 ተለዋጭ ቀጠሮ መያዙ ታውቋል።

3) አቶ መላኩ ተፈራ፦

በዋስትና በተለቀው ጉዳያቸውን ከውጪ ሆነው የሚከታተሉት አቶ መላኩ ተፈራ በእለቱ ቀረበዋል። 

ዐቃቤ ህግ በተከሳሽ በኩል ቀደም ሲል ለቀረበው የሰነድ ማስረጃ አስተያየት ይዞ እንዲቀርብ ችሎቱም ለጥር 01/2017 ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

4) አበባው ፍቃዱ እና
5) ተመስገን መቻል  በተናጠል የሽብር ክስ የቀረበባቸው ሲሆን
6) ደስታው ማሞና እንዳሰኘው የተባሉ ተከሳሾች  አራቱንም ከፌ/ፖ/ወ/ም/ቢሮ ሜክሲኮ ቀርበው ጉዳያቸውን የተከታተሉና የዋስትና ክርክር ያደረጉ መሆናቸው ታውቋል።

ከታማኝ የመረጃ ምንጭ-ከስፍራው እንደደረሰን።

ጋዜጠኛ አሳዬ ደርቤ!

Ethio 251 Media

30 Nov, 09:53


በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የህዳር 20/2017 የችሎት ውሎ፦

የአማራ ማንነትን እንደ ወንጀል በቆጠረው ዐቃቤ ህግ በተለያዩ መዝገቦች ተከፋፍለው የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው በቃሊቲ እና በቂሊንጦ ማ/ቤት በግፍ እስር ላይ ከሚገኙ ተከሳሾች መካከል በእነ የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው የክስ መዝገብ 16 ሰዎችን ጨምሮ ሌሎች ተከሳሾችም ህዳር 20/2017 በፌደራል ከ/ፍ/ቤት የህገመንግስት እና ጸረ ሽብር ወንጀል ጉዳዮች ልደታ ምድብ ችሎት ቀርበዋል።

በእለቱም ዳኞች፦

1. ያዕቆብ መኩሪያ እና
2. ጌትነት መዲና በችሎቱ ተሰይመዋል።

ከከሳሽ የፌደራል ጠ/ዐቃቤ ህግ፦

1. ናትናኤል ስንታየሁ እና
2. አዲሱ ግዛው ቀርበዋል።

ከተከሳሽ ጠበቆች መካከል፦

1. ሰሎሞን ገዛኸኝ፣
2. ቤተማሪያም አለማየሁ እና
3. ታለማ ግዛቸው ተገኝተዋል።

ህዳር 20/2017 በነበረው ችሎት በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ከቀረቡት የሽብር ክስ መዝገቦች መካከል፦

1. በእነ የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው ፋሪስ (52) ሰዎች ከመካከላቸው በቃሊቲና ቂሊንጦ እስር ላይ የሚገኙ 16 ሰዎች፣
2. አስማረ ወረቀት ከቂሊንጦ፣
3. መላኩ ተፈራ በዋስትና ተለቀው ጉዳያቸውን በውጭ የሚከታተሉ፣
4. ተመስገን መቻል ከፌደራል ፖሊስ ወ/ም/ቢሮ  ሜክሲኮ፣
5. አበባው ፍቃዱ ከፌደራል ፖሊስ ወ/ም/ቢሮ  ሜክሲኮ፣
6. ደስታው ማሞና እንዳሰኘው (2) ሰዎች ከፌደራል ፖሊስ ወ/ም/ቢሮ ሜክሲኮ መዝገቦች የተካተቱ ተከሳሾች በችሎት ተገኝተዋል።

1. በእነ የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው ፋሪስ (52) ሰዎች በሌሉበት ከተከሰሱት 38 ሰዎች ውጭ በቃሊቲ እና ቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኙ 16 ተከሳሾች ማለትም፦

1.የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው ፋሪስ፣
2.የተከበሩ ክርስቲያን ታደለ ጸጋዬ፣
3.የተከበሩ ዶ/ር ካሳ ተሻገር አለሙ፣
4.ዶ/ር ጫኔ ከበደ ማማዬ፣
5.ሙሉጌታ አገዘው ልጃለም፣
6.ታደለ አሰፋ ዋቴ፣
7.ሽበሽ መኮንን ካሳሁን፣
8.ደሳለኝ እጅጉ ወርቁ፣
9.አማረ መለሰ አከለ፣
10.ሻምበል አድማሱ አለሙ ታዬ፣
11.ቴዎድሮስ ንብረት ደስታ፣
12.ዓባይ ዘውዱ ደመቀ፣
13.ከፋለ እሱባለው አያሌው፣
14.ወተቱ ደሳለኝ በቀለ እና
15.ዶ/ር ዘሪሁን ባህሪው ታደለ እና
16.መርጌታ በላይ አዳሙን ከቃሊቲ እና ቂሊንጦ ማ/ቤት ቀርበዋል።

የፌዴራሉ ከ/ፍ/ቤት በእነ የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው የክስ መዝገብ ተከሳሾች ከማ/ቤት ስለመቅረባቸው ስም በመጥራት ካረጋገጠ በኋላ መዝገቡ የተቀጠረው የፌደራል ጠ/ ፍ/ቤቱ ዐቃቤ ህግ በመሰረተው ክስ ላይ ተገድለዋል ያላቸውን ሰዎች ስም ዝርዝርን ምስክሮች የሟቾች ቤተሰቦች  በመሆናቸው ከደህንነት አንጻር መግለጽ አይገባኝም በማለት በከ/ፍ /ቤቱ ክስ አሻሽል ውሳኔ ላይ ቅር በመሰኘት ላቀረበው ይግባኝ የጠ/ፍ/ቤቱን ውሳኔ ለመጠባበቅ እንደነበር አውስቷል።

በመሆኑም ዐቃቤ ህግ በፌ ጠ/ፍ/ቤት ያስገባው ይግባኝ "ያስቀርባል፤ ያከራክራል" በመባሉ ለታህሳስ 28/2017 የተቀጠረ መሆኑን ገልጿል።

በመሃል የፍትህ ሂደቱ ሆን ተብሎ እንዲንዛዛ እየተደረገ ነው ያሉ ተከሳሾች ቀጠሮው ተገቢ አለመሆኑን በመሳቅ ስሜታቸውን ሲገልጹ ዐቃቤ ህግ ወሩን ተጠራጥሬያለሁ በማለቱ በፍ/ቤቱ ስለተፈቀደለት ከችሎት በመውጣት ስልክ ደውሎ አረጋግጦ ተመልሷል።

ይኸውም የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት በአራተኛ ቀጠሮ  ጉዳዩ ያስቀርባል በሚል ለታህሳስ 28/2017 ቀጠሮ የሰጠ መሆኑ ተረጋግጧል።

ከተከሳሾች ረጂም የግፍ እስር እና ፈጣን ፍትሕ የማግኘት ፍላጎትና ጉጉት አንጻር ምጸት ለመሰለው ለጠቅላይ ፍ/ቤቱ የተራዘመና የተንዛዛ ቀጠሮ -በተለይም ጠበቆች በጉዳዩ ላይ በአንድ ቀን ምላሽ አዘጋጅተው ለመስጠት በሚችሉበት ሁኔታ "በቂ ጊዜ ያስፈልጋቸዋል" በሚል የተሰጠውን ቀጠሮ በከፋና በተራዘመ እስር ያሉ ተከሳሾችን ነባራዊ ሁኔታ ታሳቢ ያደረገ አይደለም በሚል ቅር በመሰኘት ቀጠሮ ተሰብሮ እንዲታይላቸው አቤቱታ እንደሚያቀርቡም ታውቋል።

ይህንን ተከትሎ ከተከሳሾች መካከል እድሉን ያገኙ የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው፣ የተከበሩ ክርስቲያን ታደለ፣ የተከበሩ ዶ/ር ካሳ ተሻገር፣ ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ እና ከፋለ እሱባለው የፍትህ ሂደቱን በተመለከተ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይም አቤቱታቸውን አቅርበዋል።

በእለቱ አነጋጋሪ ከነበሩ አቤቱታዎች መካከል በተከበሩ ክርስቲያን ታደለ እና በተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው በአጽንኦት የተነሳው በችሎቱ ውስጥ በግድግዳ ላይ የተገጠመው የስለላ ካሜራ ቀረጻ ጉዳይ ይገኝበታል።

1..የተከበሩ ክርስቲያን ታደለ፦

"በችሎቱ ግድግዳ በተገጠመው ካሜራ ያለፍቃዳችን እየቀረጻችሁን ነው፤ ይህ ትክክል አይደለም፤ ለግልጽ ችሎት አስፈላጊነቱ ከታመነበት ደግሞ ሙሉ በሙሉ ቀጥታ (live) ለኢትዮጵያ ህዝብ የችሎት ሂደቱ ሊተላለፍ ይገባል" ሲሉ ተደምጠዋል።

"ለተወሰኑ ባለስልጣናት በቀጥታ እየቀረጹ ለመስጠት ስለሚሆን ይህ አካሄድ በተከሳሾች ላይ ጫና ይፈጥራል" በማለት ከፍቃድ ውጪ የሚደረግ ቀረጻን ተቃውመዋል፤ ይህ እስካልተስተካከለ ድረስም ከቀጣይ ቀጠሮ ጀምሮ ፊታቸውን ከችሎቱ በተቃራኒው አዙረው ለመቀመጥ እንደሚገደዱ አሳውቀዋል።

በተጨማሪም ከሳሽ ከእኛ በኋላ ለመጡ በርካታ መዝገቦች ክሱን እያሻሻለ የእምነት ክህደት ቃል እንዲሰጡ እያደረገ መሆኑ እየታወቀ ይህን መዝገብ በተለየ መንገድ ለማራዘም ስለምን አስፈለገው? ሲሉ ጠይቀዋል።

"መንግስታዊ ባህሪን ባልተላበሰ መልኩ ታግተን ከርመናል፤ አሁን ደግሞ በህግ ስም ስልታዊ በሆነ ሁኔታ ፍ/ቤቱን ተጠቅሞ አገዛዙ ተደራራቢ የሆነ ግፍና በደል እያደረሰብን ይገኛል። እኔ እንደ ግለሰብ ብቻ ሳይሆን የወከልኩት ህዝብ ያለኝ እንደራሴ ነኝ፤ የመረጠኝ ህዝብ አገልግሎት ማግኘት ይፈልጋል፤ እኔም እንደ ዜጋ ፈጣን ፍትህ እፈልጋለሁ" ሲሉም ተደምጠዋል።

"ይህንን ጉዳይ ያነሳሁት አስተያየት እንድትሰጡበት ሳይሆን ለአለቆቻችሁ እንድትነግሩ ነው" ብለዋል።

"አካሄዳችሁ የሚያስተምር ሳይሆን ትውልድ ቂም እንዲይዝ የሚያደርግ በመሆኑ ስለ ኢትዮጵያ ህዝብ፣ ስለትውልዱ ብላችሁ ህሊና ካላችሁ ስለህሊናችሁ ብላችሁ ግፍ መስራት ይብቃ፤ ፈጣን ፍትህ ይሰጠን" ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

የተከበሩ ክርስቲያን አያይዘውም በማንነታችን እየተፈጸመብን ያለው ስልታዊ በደል ይቁም፤ በፓርላማም ሆነ በዐቃቤ ህግ ተስፋ ቆርጫለሁ፤ ቢያንስ የምታስተሳስረን ክር እንዳትበጠስ ፍ/ቤቱ ኃላፊነቱን እንዲወጣ እጠይቃለሁ ብለዋል።

2...የተከበሩ ዮሃንስ ቧያሌው በበኩላቸው፦

"በፍትህ ሂደቱ ላይ አንድ የተለመደ አሻጥር አለ፤ ይኸውም ፍ/ቤት፣ ዐቃቤ ህግና ፖሊስ በጋራ መድረክ እየተገናኙ የእነገሌን መዝገብ እናራዝም እያሉ ነውና በደሉን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቅልን እንፈልጋለን፤ በውሸት፣ በእገታ፣ በፖለቲካ እና አማራነትን በመወንጀል ጭምር ግፍን አሳልፈናል" ያሉት ዮሃንስ አማራን ሲያይ የሚፈራ መንግሥት ነው የገጠመን ሲሉ ተናግረዋል።

"ገና ወደ ፍ/ቤት ሳንቀርብ እንደፈረደብን እናውቃለን፤ ለወራት በእገታ ላይ የከረምን በመሆናችን ጭምር ፈጣን ፍትህ ያስፈልገናል" ብለዋል።

አያይዘውም በችሎቱ ውስጥ በስለላ ካሜራ ያለፈቃዳችን እየተቀረጽን ስለሆነ ሊቆም ይገባዋል ሲሉም ተደምጠዋል።

ከአሁን ቀደም ከፍ/ቤቱ ትዕዛዝ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ በቃሊቲ ማ/ቤት በኩል እያጋጠሙን ያሉ ችግሮች እንዲስተካከሉ እየተደረገ ነው ላሉት ጥረት ችሎቱን ያመሰገኑት ዮሃንስ አሁንም ግን የሚቀሩ ጉዳዮች እንዳሉ አመላክተዋል።

Ethio 251 Media

30 Nov, 09:53


በእስር ቤቱ ውስጥ ከመኖሪያ ክፍላቸው ተነቅሎ የተወሰደው ቴሌቪዥን እንዳልተመለሰላቸው እንዲሁም የስልክ አገልግሎትም  በአንድ ክፍል ካሉ 23 ታሳሪዎች መካከል 21 የሚሆኑት በአማራነታቸው ተለይተው የተከለከሉ ስለመሆኑ ጠቅሰው የዘረኝነት አሰራሩ "የደቡብ አፍሪካ አፓርታይድ አገዛዝን ያስናቀ ነው" ብለውታል።

የቃሊቲ ማ/ቤት ከአገዛዙ የፖለቲካ አስፈጻሚነት በመውጣት ተቋማዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ እንዳልሆነ በመግለጽ ይህ አካሄዱ እንዲስተካከል፣ በቤተሰብ ላይም የበቀል በትር ማሳረፉን እንዲያቆም ነው የጠየቁት።

3...የተከበሩ ዶ/ር  ካሳ ተሻገር፦

እድሜው 13 ዓመት ከሆነው ታማሚ ልጃቸው ጋር እንዳይገናኙ የቃሊቲ ማ/ቤት ቦታ የለም በሚል ክልከላ እያደረገባቸው መሆኑን ገልጸው ፍትህ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፤ ከአሁን ቀደምም በፖሊስ የተፈጸመበትን በደልም አስታውሰዋል።

እኛ አማራዎች በልዩ ሁኔታ እየተበደልን መሆኑን ተገንዝባችሁ እየተፈጸመብን ያለውን የአፓርታይድ ዘረኛ አሰራር እንዲቆም ተቋማዊ ኃላፊነታችሁን ተወጡ ሲሉም ጠይቀዋል።

4...ጋዜጠኛ ዓባይ ዘውዱ፦

በአፈና ስር ከርመን ነው የመጣነውና ወደ ችሎት ቢያንስ ስንመጣ የመናገር እድሉን ልትነፍጉን አይገባም በማለት ጠይቋል።

ችሎቱም ምንም እንኳ በየመሃሉ እያቋረጠውም ቢሆን የፍትህ ሂደቱን በተመለከተ አስተያየቱን እንዲሰጥ ፈቅዷሏ።

የፍትህ ሂደቱ እንዲንዛዛ በመደረጉ በተከሳሾች እና በቤተሰቦቻቸው ላይ ከፍተኛ የሆነ በደል እየደረሰባቸው መሆኑን ጠቁሞ የፍትህ ሂደቱም እንዲቀበር እያደረጉ ካሉ ተቋማት መካከል ጠ/ዐቃቤ ህግና ፌደራል ፖሊስ እንደሚገኙበት ተናግሯል።

ጋዜጠኛ ዓባይ ፊቱን ወደ ዐቃቤ ህግ ዞሮ እያየ ሃሳብ ሲሰጥ ችሎቱም ፊቱን ወደ ዳኞች እንዲመልስና እንዲናገር ሲታዘዝ በበኩሉ "ለካሜራው ቀረጻ እንዲመች ነው" በማለት በምጸት በመናገሩ ተከሳሾች፣ ዳኞችንና የችሎት ታዳሚዎችን በሳቅ ስሜታቸውን እንዲገልጹ አድርጓቸዋል።

ዐቃቤ ህግ ተመሳሳይ ክስ በማዘጋጀት እና ለበርካታ ተከሳሾች ያለምንም ልዩነት ኮፒ ፔስት በማድረግ እያደለ በመሆኑ እና በግድያ የተከሰሱ ሰዎች በግፍ እስር ላይ የሚገኙበት ሁኔታ ተገድለዋል በሚል በክሱ ላይ በቁጥር ብቻ ከተገለጹት 1100 ሰዎች መካከል ቢያንስ የአንድ  እና የሁለት ሰዎች ስም ዝርዝር እንኳ ለመግለጽ ሳይችል ወደ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ማለቱ ሆን ብሎ የፍትህ ሂደቱ እንዲንዛዛ የሚያደርግበት ስልቱ መሆኑን በመጠቆም አካሄዱን ትክክል አይደለም በሚል ተቃውሟል።

በተጨማሪም "የተቃርኖ ጉዞ አይበቃንም ወይ?" ያለው ዓባይ የፍትህ ተቋማት የሌብነት ደረጃ መዳቢው ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ሳናጣራ አናስርም" ማለታቸው ቢታወስም አገዛዛቸው ግን አይደለም አስሮ ከግማሽ አመት በላይ አፍኖና አግቶ እንኳ ለማጣራት አልቻለም በማለት የፍትህ ሂደቱ ፈተና የገጠመው መሆኑን አመላክቷል።

በመጨረሻም "መግደል መሸነፍ ነው" ያሉን ጠ/ሚኒስትሩ በአማራ ህዝብ ላይ ግን በምድርና በአየር ኃይል ተደግፈው የዘር ማጥፋት እና የጦር ወንጀል እያስፈጸሙ እንደሚገኙ በመግለጽ በእርግጥም የግፍ ጽዋው ከማይሞላ ዘረኛ አገዛዝ  የተለየ ፍትህ መጠበቅ ከባድ መሆኑን ገልጿል።

"ለመሆኑ ከዚህ የአስመሳይነትና የተቃርኖ ጉዞ መቼ ነው የምንወጣው?" ሲልም ጠይቋል።

5...ከፋለ እሱባለው፦

"እየደረሰብን ካለው ማንነት ተኮር ተደራራቢ በደል አኳያ መቆጣታችን አግባብ ነው። ይህንን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ችሎቱ ሆደ ሰፊ ሆኖ ሊያዳምጠን ይገባል፤ በእርግጥም እየተረዳችሁን ስለሆነ እናመሰግናለን" ብለዋል።

አቶ ከፋለ ዐቃቤ ህግን እያዩ ሲናገሩም ዳኞች ፊትህን ወደ ችሎቱ አዙረህ ተናገር ሲሉት "ግዴለም እኔ እንኳ እድሜዬ ከፍ ያለ ስለሆነ" በማለት የተናገሩት ውስጠ ወይራ ንግግር ብዙዎችን ፈገግ ያስደረገ ነበር።

አዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ ለወራት በእገታ ስር በነበርንበት ወቅትም "ቀደም ሲል የትግራይ ተወላጆች ተገድለው በተቀበሩበት መቃብር ላይ በጫካ ተገድደን እንድንጸዳዳ ሲደረግ ቆይቷል" ያሉት አቶ ከፋለ በአማራዎች ላይ የነበረውን አሰቃቂ የእስር ቆይታም አስታውሰዋል።

በአዋሽ አርባ ወታደራዊ ካምፕ በበርካታ አማራዎች ላይ ከተፈጸመው ተደራራቢ ግፍና በደል በተጨማሪ ወደ ሰመራ በመውሰድ በስውር በማጎሪያ ክፍል ብዙዎች ታግተው አስከፊ የግፍ ጽዋን እንዲቀምሱ ተደርጓል።

ወደ ሰመራ በእስር ከተጓዙት በርካታ አማራዎች መካከል የቀድሞው የኢንሳ ባለሙያ እና የአማራ ባንክ ሰራተኛ የነበረው ኢሳያስ በላይ በፖሊስ በተፈጸመበት አስከፊ እና አሰቃቂ የሆነ በድብደባ የታገዘ ምርመራ ህይዎቱ ማለፉን የአይን እማኝ የሆኑ አባሪቹ ይናገራሉ።

በመቀጠልም ከሰሞኑ በማህበራዊ ሚዲያ የፖለቲካ እስረኛ የሆኑ አማራዎች ሶስት አመት እንዲታሰሩ በፖለቲካ አመራሩ ከላይ ተወስኗል መባሉን በእኛና በቤተሰቦቻችን ላይ ድንጋጤን ፈጥሯል፤ ወደ ፍ/ቤት መመላለሳችንም ትርጉም የለውም ማለት ነው ያሉት አቶ ከፋለ በእርግጥም ከፍትህ መንዛዛቱ አንጻር በተግባር እየተፈጸመ ይመስላል ሲሉ የተናገሩት።

በአጠቃላይ በእለቱ ችሎት የዐቃቤ ህግ ባለሙያዎች "የእኛም መብት ይከበር እየተሳደቡ ነው" በማለት ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

በተከሳሾች በኩልም አፈና በመፈጸም የፍትህ ሂደቱ ሆን ተብሎ እንዲንዛዛና እንዲጣመም በማድረግ ለስርዓቱ ብቻ የፖለቲካ ማስፈጸሚያ ሆኖ እያገለገለ ያለ ተቋምን ወክለው የተገኙ ባለሙያዎች ይባስ ብሎ በደል እንደደረሰባቸው አድርገው ማቅረባቸው ተገቢ አይደለም በማለት ቁጣቸውን ሲገልጹ ተስተውሏል።

ችሎቱም ተከሳሾች አቤቱታቸውን ሲያቀርቡ የሌላ አካልን መብት እንዳይጋፉ፣ ችሎት እንጂ የፖለቲካ መድረክም ስላልሆነ ሲናገሩ በጥንቃቄ እንዲሆን አሳስቧል።

በችሎቱ ግድግዳ ላይ የተገጠመውን ካሜራ ቀረጻን በተመለከተ ግልጽ መረጃ እንደሌላቸው የጠቆሙት ዳኞች በቀጣይ የሚመለከተውን አካል በማነጋገር መፍትሔ እንደሚሰጡበት አስታውቀዋል።

በተያያዘ በቴክኖሎጂ የተሳሰረ ስማርት ሲቲንና ተቋማትን ከመፍጠር አኳያ ከፍተኛ በጀት ተመድቦ መሰል ስራዎች እየተሰሩ ነው በሚል የቀረበው ማብራሪያ ከተከበሩ ክርስቲያን በኩል ይህ ንግግር ፖለቲካ ስለሆነ ትክክል አይደለም የሚል የተቃውሞ ምላሽ እንዲሰጡበት አስገድዷቸዋል።

በእርግጥም ከችሎቱ በኩል "ኢትዮጵያ ወደ ቀድሞ ሁኔታዋ እግዚአብሔር ይመልሳት እንጂ ግራ ነው እየገባን ያለው፤ የኢትዮጵያ መፍትሔ እግዚአብሔር ነው፤ ዳኛ ቢያዝድ መሆን የለበትም፤ ከጀርባችን ያለው እግዚአብሔር ብቻ ነው ጸልዩ ለእኛም" የሚሉ የስርዓቱንና የአገዛዙን ተስፋ አስቆራጭነትና የሁኔታውን አሳሳቢነት በግልጽ ያመላከቱ አስተያየቶች የተሰጡ መሆኑን  ለመታዘብ ተችሏል።

ከፍተኛ የሆነ የመዝገብ መደራረብ እንዳለባቸው የገለፁት ዳኞች ለአንድ ችሎት ብቻ 45 የሽብር ክስ መዝገቦች መሰጠቱ ሂደቱን እንዲራዘም እያደረገው ስለመሆኑም በተከሳሾች በኩል ግንዛቤ እንዲወሰድላቸውም አሳስበዋል።

በማህበራዊ ሚዲያ የፖለቲካ እስረኞች 3 ዓመት ይታሰሩ በሚል የፖለቲካ ውሳኔ ተሰጥቷል የተባለውም ተጨባጭነት የሌለው ነው ሲሉ አጣጥለውታል።

በመጨረሻም ጠበቆች ከተከሳሾች ንብረት ጋር በተያያዘ በተከሳሾች ተደጋጋሚ እየተነሳ ያለና ምላሽ ያልተሰጠው ጉዳይ በመሆኑ ፌደራል ፖሊስ በችሎት ተገኝቶ ምላሽ እንዲሰጥበት ፍ/ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

Ethio 251 Media

29 Nov, 18:40


አርበኛ መሳፍንት ተስፉ ስለ ኢትዮ 251 ሚዲያ...

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

https://www.ethio251media.org/be-a-member

Bank Acct Info: Chase Bank
Account number 675535275
Routing number 322271627
Zelle : [email protected]
Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

29 Nov, 17:45


የአማራ ፋኖ በጎንደር ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ባዬ ቀናው ስለ ኢትዮ 251 ሚዲያ…

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

https://www.ethio251media.org/be-a-member

Bank Acct Info: Chase Bank
Account number 675535275
Routing number 322271627
Zelle : [email protected]
Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

29 Nov, 16:40


https://www.youtube.com/live/l-L9HJnPG7M?si=oJjMgG4H3oVei8fO

Ethio 251 Media

29 Nov, 16:37


ዋርካው ምሬ ወዳጆ ስለ ኢትዮ 251 ሚዲያ


ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

https://www.ethio251media.org/be-a-member

Bank Acct Info: Chase Bank
Account number 675535275
Routing number 322271627

Zelle : [email protected]

Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

29 Nov, 16:36


https://www.youtube.com/live/l-L9HJnPG7M?feature=shared

Ethio 251 Media

29 Nov, 14:09


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ ተጠናክሮ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ወልድያ ዙሪያ ከባድ ተጋድሎ በማድረግ ታላቅ ድል ተጎናፀፈ::

የሰሜን ወሎ ዞን ዋና መቀመጫ ወልድያ ከተማና በዙሪያው በርካታ ተጋድሎዎችን እያደረገና በርካታ ድሎችን እየተጎናፀፈ የሰነበተው በዋርካው ምሬ ወዳጆ የሚመራው የአማራ ፋኖ በወሎ ከትናትና ህዳር 19/2017 ዓ.ም ማለዳ ጀምሮ እስከ ዛሬ ንጋት ለ24 ሰዓት ቀንና ሌሊት ያለማቋረጥ በተደረገው ተጋድሎ 49ኛና 52ኛ ክፍለጦር የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ የጠላት ሃይል በርካታ ሙትና ቁስለኛ ሆኖ ይዞታወቹን ለጀግኖቹ አስረክቦ እንደተለመደው ፈርጥጧል::

በተጋድሎው አሳምነው ክፍለጦር አራት ሻለቆችና ሃውጃኖ ክፍለጦር ሁለት ሻለቆች የዞብል አምባ ክፍለጦር ሁለት ሻለቆችን ተጠባባቂና ደጀን አድርገው የተፋለሙ ሲሆን በጠላት በኩል ሁለት ክፍለጦር አሰልፎ በርካታ ተጋድሎዎች ተደርገዋል::

በፍልሚያዉም የጠላት ሃይል ከፋኖ መካናይዝድ በኩል የሚወነጨፍበትን ሞርተር መቋቋም ያቃተው ሲሆን ወልድያ ስታዲዮምና ማር ማቀነባበሪያው ላይ ያለ ጠላትም የሞርተር ጥቃት ተፈፅሞበት በርካታ ሙትና ቁስለኛ ሆኗል::

ተጋድሎው በበርካታ የወሎ ቤተ-አምሐራ ቀጠናዎች በበርካታ የደፈጣና የመደበኛ ዉጊያ ድሎች ታጅቦ እየተደረገ ያለ ሲሆን በቅርቡም የወረዳና የዞን ከተሞችን መቆጣጠርን ያለመ ተጋድሎ የሚደረግ ይሆናል:: በእስካሁኑ ተጋድሎዎችም ከራያ አላማጣ ዋጃ እስከ ወልድያና ደሴ የፌደራል መንገድ እየተባለ የሚጠራዉን መስመር ጨምሮ በርካታ የቀጠናው አካባቢዎች በፋኖ ቁጥጥር ስር ያሉና የህዝብ አስተዳደርም የተዘረጋበት ሁኔታ እንዳለ የሚታወቅ ነው::

በቀጣይም የህልዉና ተጋድሎው እስከ ድልና ነፃነት ተጠናክሮ ይቀጥላል!

ድል ለፋኖ
ድል ለ አማራ ህዝብ
የ አማራ ፋኖ በወሎ
ህዳር 20/2017 ዓ.ም

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Nov, 09:57


ደንበጫ የጠላት መቅጫ
~~~~~~~~~
፲፩ኛው ቀን የተጋድሎ ውሎ ~~~~~~
፲፩ኛውበቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ሁለት ሳምንት አለፈው ያለማቋረጥ ውጊያ ማድረግ ከጀመረ!!
ይህም ሆኖ ግን ጠላት እንደ ቅጠል እየረገፈ ነው።
አስራ አንድ ቀን ሙሉ የእጅ በእጅ ውጊያ ሲያደርግ የነበረው የኢንጅነር ክበር ተመስጌን ብርጌድ ትናንት ምሽት እስከ አንድ ሰዓት ድረስ ሲፋለሙት አምሽተው ጠላት በየጫካው ከተበተነ በኃላ ለአይን ሲነሳ ፋኖ ከምሽጉ ወጥቶ ቦታውን ሲይዝ ጠላት እግሬ አውጭኝ ብሎ ፈረጠጠ።

ዙ23 ካልመጣና ሽፋን ካልተሰጠን ተከበናል አድኑን ያለው የወንበዴው ቡድን ከየጨረቃ ተነስቶ አንድ ዙ 23 አስከትሎ የተመታበትን ኃይሉን ሊያወጣ ቢመጣም ያሰበው አልተሳካለትም!!!

ዙ-23 የተበተነን ጦር ማስለቀቅ አይችልም።ይህንም በተግባር ደንበጫ ላይ አይተናል።

አንድ ጀግና ከእነ ጎጆቹ ጋር በጨለማ ተስቦ ዙ 23ቱን ዶግ አመድ አርጎ ሹፌርና ረዳቱንም እስከወዲያኛው አሰናበታቸው።

ጠላት ተደናግጦ ዙ-23 ሲቃጠል እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደ መጣበት ፈረጠጠ።ቀኑን ሙሉ ሲመታ የዋለው ኃይልም ከተበታተነበት ተለቃቅሞ የያዘውን ሸንሸል ተተኳሽ ሁሉ በየቦታው እየጣለ ራሱን ለማዳን ፈረጠጠ።
እጅግ ብዛት ያለው ተተኳሽና የቡድን መሳሪያ ከአነ ሸንሸሉ ተተኳሹን ጥሎ ፈረጠጠ።
ተመቶ የተቃጠለው ዙ 23 ከጥቅም ውጭ ሆኖ እየጎተተ ይዞት ተመልሷል።

#በሺ አለቃ ይርሳው ደምስ የሚመራው የደንበጫ ፋኖ ግን ምድራዊ ድሮን በመባል ቢጠራ ያንስበታል ይሆን?እረ አያንስበትም አስራ አንድ ቀን ሁሉ ባደረገው ውጊያ ኮለኔሎችን፤ሻለቃዎችን፣
ሻምበሎችን፣ኮማንደሮችን ሁሉ ደምስሷል።

በርካታ ተተኳሾችንም ለመማረክ ችሏል።
ታሪክ በእጃቸው መስራት ልማዳቸው የሆኑት የኢንጅነር ክበር ተመስጌን ብርጌድ ዛሬ ጠላትን አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው እይዘዋለሁ ያለውን ቦታም ሳያየው አብዛኛውን ደምስሰው የተረፈውን መልሰው ልከውታል።

በየመንገዱ እየፈረጠጠ ሳለ የቆሰለበትን እየረሸነ ይጓዝ ነበር።ሬሳውንም የሚያነሳበት መኪና ስላልነበረው በየቦታው ወድቆ ቀርቷል።
ድል በድል የሆነው የኢንጅነር ክበር ተመስጌን ብርጌድን አስራ አንድ ቀን ተዋግቶ ዛሬም ሌላ ስራ ላይ ነው።

ይሔ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክፍለ ጦር ግን ምን አይነት ብርጌዶችን ነው በውስጡ የሰበሰበው አለኝ አንድ ወዳጄ በውስጥ መስመር መጥቶ?

አይ ወንድሜ ታቃለህ ያኔ መስከረም 21/01/2016 ዓም ከተመሰረቱት ክፍለ ጦሮች ከተመሰረተበት ቀን አንስቶ ያለምንም ማመንታት ራሱን በብዙ ነገር ሲያደራጅ የነበረ ክፍለ ጦር በኃላም ጥር ሶስት ጠቅላላ ጉባኤ በማድረግ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት የውስጥ አደረጃጀቶችን ያለማንም ጣልቃ ገብነት በመርህ የሚሰራ ጦር ለመገንባት ቃል ገብቶ ወደ ስራ ከገቡት ጠንካራ ክፍለ ጦር አንዱ ነው።

በዚህ ደግሞ ከፊት ያሉት መሪዎች እንደ ወርቅ በእሳት የተፈተኑ የረዥም ጊዜ የትግል ልምድ ያላቸው ጀግና መሪዎች ያሉበት ዳሩ ግን በጀግንነታቸው ልክ ስራቸውን ለአዓለም ያልታወቀላቸው በስራ ብቻ የሚታወቁ #ዝምኛ ገዳይ የሚባሉ አናብስቶች የበዙበት ስለሆነ በስሩ ያሉ ብርጌዶችንም እንዲሁ መንፈሰ ጠንካራ ናቸው ስለው በደስታ ወደቀ።
ገና ታሪክ በክንዳችን እና በፈጣሪ እረዳትነት እንሰራለን።ይሔ ክፍለ ጦር ታምረኛ ነው።የአራት ኪሎው ባንዳ አጥብቆ ከሚፈራቸው ክፍለ ጦሮች ግንባር ቀደሙ ነው ማለት እችላለሁ።

ደብረ ማርቆስ ላይ ወሽቆ የሚገኘው የካድሬ ስብስብ ሲተኛም ሲነሳም ሲበላም ሲራመድም በአዕምሮው የሚመጣበት የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክፍለ ጦር ነው።
በዚህ ክፍለ ጦር ውስጥ ስድስት ብርጌዶች አሉ።ሁሉም ግን እጅን በአፍ የሚያስጭን ታሪክ በየቀኑ ይሰራሉ።ፈክረው ገብተው ያሰቡትን ጀብድ የሚፈፅሙ የድንቅ ብርጌዶች ስብስብ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክፍለ ጦር።

ኢንጅነር ክበር ተመስጌን ብርጌድን አለማድነቅ ማለት የአማራን ትግል እንዳለመደገፍ ይቆጠራል።

ኢንጅነር ክበር ተመስጌን ብርጌዶችን አመስግኑልኝ!!!

አዲስ አብዮት
አዲስ ድል
አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
በወንበዴዎች ወንበር የማይናውዝ አዲስ ትውልድ በክንዳችን እና በአንደበታችን እንፈጥራለን።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ መ/ር ታደገ ይሁኔ(ሸርብ)

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Nov, 09:38


በእስቴ ግንባር እርምጃ የተወሰደበት የአገዛዙ ሰራዊት ኪሳራ ደርሶበታል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር የጉና ኮፍለጦር እስቴ ደንሳ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ማረው ክንዱ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት .....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 15:25


ከባህርዳር መነሻውን አድርጎ ዘጌ ላይ ሀይል በመጨመር የተንቀሳቀሰው የጠላት ቡድን በተወሰደበት እርምጃ ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም 1ኛ ክፍለጦር የባህርዳር ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሀብታሙ የሱፍ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 15:17


በወሎ ቀጠና ተጋድሎዎች ቀጥለዋል።

የአገዛዙ በአውደ ውጊያ ያጣውን ድል በአዳራሽ ዲስኩር ለማሳካት ቢሞክርም እንዳልተሳካለት ተገልጿል።

የጋራ አንድነት እንዲመጣ እየሰራን ነው በቅርቡ እንጨርሳለን ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ባደረገው ቆይታ ገልጿል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 15:02


በሸዋ ቀጠና የአገዛዙ ተልዕኮ አስፈፃሚና አመራር አባላት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት የመሀመድ ቢሆነኝ ክፍለ ጦር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ምናሉ ታደሰ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 14:24


በሰላሌ የተፈፀመው አፀያፊ ድርጊት የአማራ ፋኖ ስልጣኑን እንደሚረከበው ያወቀው ብልፅግና በህዝብ ለህዝብ ግጭት ህልውናውን ለመጠበቅ የፈፀመው ወንጀል ነው።

ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 14:03


በማህበራዊ ሚዲያ ፋኖ የፈፀመው በማስመሰል የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛና የብልፅግና አገዛዝ የለመደው የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ ካርዱ መሆኑን በደራ ቀጠና የሚንቀሳቀሰው አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ጀነራል አሳምነው ጽጌ ብርጌድ ገለፀ።

በትናንትናው እለት በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር የዋለው የአማራ ፋኖን ልዕልና የማይወክል  አሰቃቂ ምስልን በተመለከተ ከአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሳምነው ፅጌ ብርጌድ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ መምህር ፋኖ ጌታቸው አበበ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ፋኖ መምህር ጌታቸው ተጨባጭ መረጃ የሌለው የደራ አማራንና ከክልሉ ውጪ ያለውን አማራ ለመጨፍጨፍ በአገዛዙ ኃይሎችና ፅንፈኞች የፈፀሙት ሴራ ነው ሲል ጉዳዩን ገልፆታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 13:55


በደቡብ ጎንደር ጋይንት ዙሪያ ከበባ ለመፈፀም የተንቀሳቀሰው የአብይ አህመድ ሠራዊት አጋጥ ሚካኤል በተባለ ቦታ ላይ በደፈጣ ተደምስሷል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ከፍያለው ደሴ በሰሞንኛ ተጋድሎዎች ዙሪያ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 13:38


“ፋኖ ኃይማኖታዊ መንግስትንም ሆነ መንግስታዊ ኃይማኖትን እንደሚቃወም ሊታወቅ ይገባል” ፋኖ ዳዊት ቀጠላ

ተስፋ የቆረጠው ይሄው "መንግሥት" ነኝ ባይ ወንበዴ አሁንም ሌላ ነውር መፈጸሙን ይቀጥላል። የሥልጣን እድሜ ማረዘሚያ መድኃኒቱ ይሄው ስለሆነ "ያድነኛል" የሚለውን ሁሉ መጠቀሙ የማይቀር ነው። እኛ ግን ዛሬም እንላለን "በያዝነው ሀቅና እውነት አረመኔነትን የሕይወቱ መመሪያ ያደረገውን ስርዐት በጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ እንቀብረዋለን!" ይህ ብቻ አይደለም የዚህ ስርዐት ተባባሪዎች ሁሉ በምድሪቱ ግፍ ተጸንሶ ተወልዶ እንዲያድግ የሚሰሩ ናቸው እነሱንም እንፋረዳቸዋለን።

በየጊዜው ስለምታመጡት የፖለቲካ ሴራ የሚደነግጥ አማራ የለም ይህ ብቻ አይደለም ይህንን ሴራ የተረዱ ሌሎች ወገኖቻችንም የዚህ የተቀደሰ ትግላችን ደጋፊዎች ናቸው። በሁሉም ኢትዮጵያውያን ኅሊና በጉጉት በብዙ ተስፋ የሚጠበቀው ተናፋቂው ፋኖ ስርዐቱ እየተሽመደመደ መሆኑ በገባው ጊዜ ከትውልዱ ልብ ውስጥ የወጣ መሆኑንም በተረዳ ጊዜ ብዙ ኦሮሞዎችን እያረደ ስለፍትህ በሚታገለው አማራ ህዝብ ላይ ጥላቻን ለማጽናት የሚያደርገው የተስፋ መቁረጥ ቁማር በእኛ ዘንድ አይሰራም። በዚህ የፍትህ ትግላችን ጉዞ ውስጥ በኦሮሞ ስም ስልጣን ይዣለሁ የሚለው ይሄው ነውረኛ ስርዐት ወክዬዋለሁ ለሚለው ህዝብ እንኳን የሚራራ አይደለም።

የኦሮሞ ማኅፀን ያስገኟቸውን ጀግኖች በኦሮሞ ባልል ትልቅ ክብር ያላቸውን አባ ገዳዎች ሳይቀር ሰብአዊ ክብራቸውን እያዋረደ እጅና እግሮቻቸውን አስሮ አፋቸውን ለጉሞ በግፍ እየገደለ ለቃዠው የፖለቲካ ፍላጎቱ ጥም ማርኪያ እንዲሆን ያልፈጸመው ግፍ የለም። ብዙ የጥበብ ሰዎችን የገደለ ይሄው ስርዐት ነው በመላው ኦሮምያ ቤት ለቤት እየዞረ ነፍጠኛ ስልጣናችሁን ሊቀማችሁ ነው እያለ በሚያደርገው ቅስቀሳ አልሳካ ያለውን ነገር ሁሉ በሌላ መንገድ ከዘር ባሻገር ሃይማኖታዊ ቀውስ በመፍጠር እርስ በእርስ የማጫረሱን የዘመናት ህልሙን ለማሳካት የሚያደርገውን በባህሪ የተዋሀደውን ተንኮል እየገለጠ ያለበት ሁኔታ በመሆኑ ህዝቡ ሊነቃ ይገባል።

ፋኖ ክርስቲያናዊም ይሁን እስላማዊ አጀንዳ የለውም። ፋኖ ዓላማው ግልጽ ነው ጠላት ብሎ የፈረጀውም ህዝብ የለም አማራ ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ ጋር በልኩ እንዲኖር ነው የምንታገለው። ባለፉት ጥቂት በማይባሉ ዓመታት በተጻፈና በተሰነደ ስሁት ትርክት ምክንያት ህዝባችን በያለበት ብዙ ስቃይና መከራ እየገፋ በመሆኑ ይህንን መንግሥት መር (state sponsored) የሆነ ጥፋት ለመቀልበስ በነፍጠኝነት ታሪካችን ነፍጥ አንግበን እየታገልነው ያለነው ይህንኑ ታሪካዊ ጠላታችን የሆነ ገዢውን ስርዐት ነው።

እውነትና ፍትህ በዚች ምድር እንዲዘረጋ የሚፈልጉ ወገኖች ሁሉ የጠራና ግልጽ የሆነውን ዓላማችንን ተረድተው ያግዙናል። ለማንኛውም ፋኖነት አሸናፊነት ነው ይሄው ገዢ ቡድን ግን መሸነፉ አይቀሬ መሆኑ ሲገባው እንዲህ ዐይነት የሴራ ካርድ በመምዘዝ የተለመደ ቅሌቱን እያጋለጠ ይገኛል። ከፊቱ የሚታየውን ሽንፈት በፍርሀት ቆፈን ውስጥ ሆኖ በጀሌዎቹ በኩል በህዝብና ህዝብ መካከል የከፋ ልዩነት በመፍጠር የስልጣን እድሜ ለማራዘም ቢያቅድም ይህ ቅዠት ግን በእውነት ሚዛን ተመዝኖ የቀለለ ነው የምናዝነው ዛሬም በአማራ ላይ አመጽ ለማስነሳትና የትናንቱን መሳሪያዎቹን አማራ ጠል ቡድኖቹን በህዝባችን ላይ ካራ አሲዞ ለማሰማራት ንፁሃንን ማረዱ ነው። ይህ የውርደት ካባ ያለፈበት የፖለቲካ ቁማር ፋሽን ነውና ሳይረፍድብህ ለነፃነት በነፃ ደሙን እያፈሰሰ፣ ስጋውን እየቆረሰና አጥንቱን እየከሰከሰ ሃገር ለማፅናት ለሚታገለው #ፋኖ እጅህን ብትሰጥ መልካም ነው ።

ፋኖ ዳዊት ቀፀላ
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ቀጠናዊ ትስስር መምሪያ ኃላፊ

Ethio 251 Media

21 Nov, 13:37


የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ደረጄ በላይ እና ፋኖ ኪሩቤል ጎቤ በወቅታዊ የትግል እንቅስቃሴ ዙሪያ እና የአገዛዙን ቁመና በተመለከተ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ያጋሩት የምስል መግለጫ በጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር ቀርቧል !

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 13:25


የአማራ ጎንደር ዕዝ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የአምበሳው ሊቦከምከም ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ጌጤ ጀምበር በግንባር ተጋድሎዎች ዙሪያ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Nov, 13:16


የግፍ እስረኞች ማከማቻ የነበረው አንገረብ ማረሚያ ቤት በፋኖ ሃይሎች ተሰብሯል።

ኦፕሬሽኑን ያከናወነው የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ጃንተከል ብርጌድ ከ22 በላይ የግፍ አስረኞችን ሲያስለቅቅ ከ10 የሚበልጡ የአገዛዙ ኃይሎች እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ አደረጃጀት ዘሮፍ ኃላፊ አርበኛ በላይነህ ዘለቀ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 19:26


“የአገዛዙ ሴራ ይከስማል!”ፋኖ

በማህበራዊ ሚዲያ ፋኖ የፈፀመው በማስመሰል የተሰራጨው መረጃ ሀሰተኛና የብልፅግና አገዛዝ በለመደው የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ ካርዱ መሆኑን በደራ ቀጠና የሚንቀሳቀሰው አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ጀነራል አሳምነው ጽጌ ብርጌድ ገለፀ።

ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ሲዘዋወር የዋለው የአማራ ፋኖን ልዕልና የማይወክል  አሰቃቂ ምስልን በተመለከተ ከአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሳምነው ፅጌ ብርጌድ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ መምህር ፋኖ ጌታቸው አበበ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ታንክና ባንኩን ይዞ በአማራ ህዝብ ላይ የተቀናጀ ወረራ መፈፀም ከጀመረ አንድ ዓመት በላይ የሆነው የአብይ አህመድ ብልፅግና አገዛዝ “በአማራ ፋኖ የህልውና ትግል አከርካሪው ሲመታ የህዝብ ለህዝብ ግጭትና የሀይማኖት ግጭት ለመፍጠር አልሞ እየሰራ ይገኛል” ሲል የገለፀው ፋኖ መምህር ጌታቸው ተጨባጭ መረጃ የሌለው የተቀነባበረ ድምፅና ምስል የተካተተበት የደራ አማራንና ከክልሉ ውጪ ያለውን አማራ ለመጨፍጨፍ የተፈበረከ የፈጠራ ትርክት ነው ሲል ገልፆታል።

በማህበራዊ ሚዲያ የሚዘዋወረውን ምስል እንኳንስ እኛ ልንፈፅመው ምስሉን እንደማንኛውም ሰው በማህበራዊ ሚዲያ ሲዘዋወር ነው የተመለከትነው። ይሄ ጠላቶቻችን የሰሩት የሴራ ዶክመንተሪ ነው። ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ተግባሮችን እየፈፀሙ ተዋልዶና ተጋምዶ የሚኖረውን የኦሮሞና የአማራን ህዝብ የእርስ በእርስ ግጭት ውስጥ በማስገባት ስልጣናቸውን ለማስጠበቅና የጥፋት ፍላጎታቸውን ለማስፈፀም በህዝባችን ቅስቀሳ ሲያደርጉ እንደነበር ይታወቃል ያለው ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው፣ ይሄኛው አስነዋሪ ድርጊትና ተግባርም በአማራ ፋኖ የትግል ሜዳ ሽንፈት የገጠመው ብልፅግናና ግብረአበሮቹ ህልውናቸውን ለማስጠበቅ ህዝብን በህዝብ ላይ ለማነሳሳት የሚያደርጉት ሙከራ እንደሆነ ገልጿል።

የጥፋት ቡድኑ ብልፅግናና የአንድ ሳንቲም ሌላኛው ገፅታው የሆነው ብልፅግና ያደራጀው የሸኔ ኃይል በህዝባችን ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ከመግደል አልፈው ፤ ወጣንበት የሚሉትን የኦሮሞ ማህበረሰብ ሲገድሉና ሲጨፈጭፉ የነበሩ ቡድኖች የፈፀሙት ተግባር እንደሆነ ገልፆ፣ ይህንን የደራም ህዝብ ሆነ መላው ኢትዮጵያዊ የሚገነዘበው ሀቅ ነው ብሏል። በቅርቡ በዚሁ ቀጠና አንድ የመስጊድ ኢማም በሸኔ ሃይሎች ከመላ ቤተሰቦቻቸው ጋር መገደላቸው ይታወቃል። የአማራ ፋኖ የትግል አስተምህሮ ይህን መሰል ተግባር ፍፁም የሚጠየፈው እንደሆነም አንስቷል።

የደራ አማራ  በዚሁ ቡድን ሲገደልና ሲጨፈጨፍ የቆየ መሆኑን የገለፀው ፋኖ ጌታቸው ቡድኑ መንገድ ሲዘጋ፣ የእምነት ተቋማት ሲያቃጥል፣ ተቋማትን ሲዘርፍ ፣ እገታ በመፈፀም ገንዘብ ሲቀበል፣ አሰቃቂ ግድያዎችን ሲፈፅም እንደነበር እኛ ብቻ ሳይሆን የሀገር ውስጥም ሆነ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት የሚያውቁት እውነት ነው፣ አሁንም ጉዳዩን ለማጣራት ፍላጎት ያለው የሰብዓዊ መብት ተቋም ማጣራት እንደሚችል እየገለጽን ለዚህም ሙሉ ጥበቃ እንደምሰጥ መግለጽ እንፈልጋለን ሲል የብርጌዱ የሕዘብ ግንኙነት ኃላፊ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ይሄ ድርጊት የደራ አማራንና ከክልሉ ውጪ ያለውን አማራ ለማጥፋት የኦሮሞ ብልፅግና አመራሮች ከሸኔ ሃይሎች ጋር ተባብረው የሳቡት የጥፋት ካርድ ነውም ብሏል።

በመራቤቴ አውራጃ በደራ ቀጠና የሚንቀሳቀሰው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በኦሮሞ ንፁሃን ላይ ጥቃት ሊፈፅም ቀርቶ በአውደውጊያ የሚማረኩ በብሄር ኦሮሞ የሆኑ የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ወደ ቤተሰቦቻቸው እንደሚልካቸውና ፍፁም በዚህ ሰይጣናዊ ተግባር ሊሳተፍ እንደማይችል ገልጿል። በደራ ጉንዶ መስቀል ሰለልኩላ የተፈፀመው ድርጊት የደራ አማራን ለማጥፋት የታቀደና የእምነት ተቋማትን የጥቃት ሰለባ ለማድረግ በአክራሪ የኦሮሞ ፅንፈኞች የተፈጠረ የበሬ ወለደ ትወና ነው ሲል ገልፆታል።


የምንዋጋው በአማራ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት አዋጅ ያወጀውን የአብይ አህመድ አገዛዝ እንጂ የትኛውንም ብሄረሰብና ቡድን አይደለም ሲል  የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለጦር አሳምነው ፅጌ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ መምህር ጌታቸው አበበ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በሰጠው ቃለ-ምልልስ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

Ethio 251 Media

20 Nov, 18:53


ሰበር ዜና!

“በወገን ሠራዊት ላይ አፈና ለመፈፀም የተንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል በደፈጣ ተደምስሷል።” አርበኛ ከፍያለው ደሴ

የአማራ ፋኖ በጎንደር የገብርዬ ክፍለ ጦር በደቡብ ጎንደር ቀጠና ከአገዛዙ ወንበር አስጠባቂ ኃይል ጋር ከፍተኛ ተጋድሎ በማድረግ ድል ማስመዝገቡን አርበኛ ከፍያለው ደሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በሰጠው ቃለ ምልልስ ገልጿል።

በደቡብ ጎንደር ጋይንት ዙሪያ ከበባ ለመፈፀም የተንቀሳቀሰውን የአብይ አህመድ ሠራዊት አጋጥ ሚካኤል በተባለ ቦታ ላይ ደፈጣ በመጣል ነበልባሎቹ ደምስሰውታል።

በአውደ ውጊያው በርካታ የስርዓቱ ወታደሮች እጅ እየሰጡ እንደሆነ የገለፀው አርበኛ ከፍያለው 13 ምርኮኞችን በቁጥጥር ስር ሲያወሉ በርካቶች መደምሰሳቸው ታውቋል። በዚህ ግንባር የስርዓቱ ዲሽቃ ተኳሽበቅርብ ርቀት ሊደመሰስ ባለበት ሁኔታ ውስጥ 4 የእጅ ቦምብ ወርውሮ ዲሽቃውን ጥሎ ሲፈረጥ፤ 7 መንገድ ከተባለ ቦታ ወደ ነገላ አቅጣጫ 50 የሠራዊቱ አባላት የፋኖን የውጊያ በትር መቋቋም ስላልቻሉ አዳራቸውን ጠፍተው ማደራቸውም የብልፅግና አመራሮችን ማስደንገጡን ገልጿል።

በጎንደር ቀጠና የብልፅግና ከፍተኛ የሠራዊት አመራሮች ጭምር ስምሪት የሚሰጡበት ከፍተኛ ተጋድሎ እየተደረገ እንደሚገኝ የገለፀው አርበኛ ከፍያለው እሰሰካሁን 20 ቀን ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።

ከዚህ ባሻገር የአገዛዙ ሠራዊት እየከዳና እየተማረከ ሲገኝ ፍቃድ የተከለከለ የብልፅግና ሠራዊት አባል 3 የስርዓቱ ወታደራዊ አመራሮች ላይ እርምጃ ወስዶ ወደ ፋኖ እንደተቀላቀለ ያነሳው አርበኛው የብልፅግና የታህሳስ 30 ፋኖን የማጥፋት ዕቅድ የስርዓቱ የቁም ቅዠት እንደሆነና ሠራዊቱ እየተበተነበት እንደሚገኝ የአማራ ፋኖ በጎንደር የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ እና የገብርዬ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ከፍያለው ደሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 16:49


https://rumble.com/v5rc8nz--20-november-2024-251-zare-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

20 Nov, 11:53


የአማራ ፋኖ በጎጃም በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች በ18 ግንባር የአገዛዙ ኃይል እየተመታ ይገኛል።

ደምበጫና አዲስ ቅዳም ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል። በርካታ የቡድንና የነብስ ወከፍ መሳሪያ ተማርኳል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ የአገዛዙ ሠራዊት እንቅስቃሴና የፋኖ ድሎችን በተመለከተ  ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 11:35


በዳንግላ ከተማ አገዛዙ ትምህርት ቤቶችን አወደመ !

በጎጃም የዳንግላ አድባራ የመጀመሪያ ጀረጃ ትምህርት ቤት በአገዛዙ ውድመትና ቃጠሎ ደርሶበታል።

ተከታተሉት......

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 10:58


በጎጃም ቀጠና የግንባር ተጋድሎዎች ሲቀጥሉ የአገዛዙ የጥፋት ተግባራትም በትምህርት ቤቶችና መሠል ተቋማት ላይ ቀጥሏል።

በጭምባ የትምህርት ተቋማት በአገዛዙ ኃይል ሲወድሙና ሲዘረፉ አገዛዙ በቆየባቸው ጊዜያት የማህበረሰብ እንግልት ሲፈጥር እንደነበረም ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የቢትወደድ አያሌው መኮንን ብርጌድ ቀኝ አዝማች ባብል ደስታ ብርጌድ ዋና አዛዥ ፋኖ ካሳሁን አድማሱ አገዛዙ በፈፀመው ውድመት ዙሪያ ያጋራው መልዕክት ለኢትዮ 251 ሚዲያ ደርሷል።

ተከታተሉት .....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 10:48


በጎንደር 4 ኛ ቀኑን የያዘው የእስቴ ስማዳ የግንባር ተጋድሎ ቀጥሏል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አሸናፊ ወንድወሰን ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር በግንባር ተጋድሎ ዙሪያ ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 10:14


በጎንደር ግንባር ደቡብ ጎንደር ቀጠና የአገዛዙ ከፍተኛ  ወታደራዊ መኮንኖች የተሳተፉበት ውጊያ እየተካሄደ ነው።

የእቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር አንበሳው ሊቦከምከም ብርጌድና አስቻለው ደሴ ብርጌድ ከጠላት ጋር ከፍተኛ ተጋድሎ አድርገዋል።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ እቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ መልካሙ ጣሴ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 09:25


ከበባ መፈፀም ያሰበው የአገዛዙ ኃይል ተደጋጋሚ ጉዳት እያስተናገደ እንደሚገኝ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የአስቴጉማ ተራራ ክፍለጦር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አብርሃም አሰፋ በግንባር ተጋድሎዎች ዙሪያ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

20 Nov, 09:15


የደብረ ማርቆሱ ጥቃት !
ህዳር 11 ቀን 2017 ዓም ኢትዮ 251 ሚዲያ። ሚዛን አስጠባቂዋ የንጉስ ተክለ ሐይማኖት ብርጌድ በደብረ ማርቆስ።

በዛሬው እለት ከቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ተወርዋሪ ንስር ኮማንዶ ጋር በመሆን ከለሊቱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ለሊቱ 10:00 ሰዓት ድረስ በደብረ ማርቆስ ከውኃ ጋን እስከ  የብራጌ  በተደረገ የደፈጣ ውጊያ የብልፅግና ወንበር አስጠባቂው የአድማ ብተና እና ሚኒሻ ኬላ ላይ የነበረ ሁሉ ተደምስሷል።

የብልፅግናው ጀኔራሉ ከዚህ በኋላ ደብረ ማርቆስ ላይ የጥይት ተኩስ አትሰሙም እያለ ሲቀልድ እንዳልነበረ ዛሬ ሌላ ታምር ተሰርቶበት አድሯል።

ከአማራ ህዝብ ጎን የቆሙ ከውስጥ ሆነውም የጠላትን ኃይል እንዲፈርስ ከፍተኛውን ስራ እየሰሩ ያሉ አድማ ብተና እና ፖሊስ በተሰጡት መረጃ መሰረት ፋኖ ስራውን ሰርቷል።

በዚህ የተደናበረው የጠላት ኃይል ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ንጉስ ተክለሐይማኖት ብርጌድን እይዛለሁ ጮቄንም እይዛለሁ ብሎ ከሳምንት በላይ የተንቀሳቀሰው የአብይ አህመድ አራዊት ሰራዊት ቡድን ከየቦቅላ፣ከቀይ አቦ እና ደብረዘይት ከባቢ ሲቀጠቀጥ መሰንበቱ ይታወቃል።

በመሆኑም ዛሬ ደብረ ማርቆስ ላይ በተሰራው ታምር ይሔ አራዊት ሰራዊት እግሬ አውጭኝ በማለት ሁሉንም ቀጠና ለቆ ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ጉዞ በመጀመር ደብረ ማርቆስ ተያዘብኝ በማለት ይዞት የሔደውን ስንቅ እንኳ ሳይቋጥር በለሊት ደብረ ማርቅስ ገብቶ አድሯል ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ መ/ር ታደገ ይሁኔ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

የንጉሱ ልጆች እና ተወርዋሪ ንስር ኮማንዶዎች የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ቀኝ እጅ መሆናቸውን ያሳዩበት የዛሬው ውጊያ የጠላትን ቅስም ሰብረውት አድረዋል።

ጠላት ዳግም ወደየቀበሌዎች ወጥቶ በሰላም መመለስ እንደማይችል የተመለከተበት፣እኛ ፋኖዎች ደግሞ ጠላት የመጨረሻ እስትንፋሱ የቀረ መሆኑንና ምንም አይነት እርባና ያለው ወታደር እንደሌለው ያረጋገጥንበት አዳር ነበር።

እንግዲህ ከቁይ፣ከየሰንበት፣ከደብረ ማርቆስ፣ከደብረ ዘይት ተሰባስቦ የቦቅላን ይዞ የነበረው ኃይል ፤ የየሰንበቱ በጀርቤው ከሁለት ቀን በፊት ሲቀጠቀጥ ተመልሶ ወደ ካምፑ ሉማሜ ሲገባ የደብረ ዘይቱ ደግሞ ቀኝ አቦ ላይ አይቀጡ ቅጣት ሲቀጣ ከደብረ ማርቆስና ከቁይ የመጣው ደግሞ እግሬ አውጭኝ ብሎ ወደየመጣበት መገስገሱ ታምር ነው።

ፋኖ ይችላል፣የትኛውም ምድራዊ ኃይል የፋኖን በትር መሸከም አይችልም የምንለው ያለምክንያት አድለም ።

ያም ሆኖ ያ ከደብረ ማርቆስም ከደብረ ዘይትም ተንቀሳቅሶ የነበረው የጠላት ኃይል ጠቅልሎ ማርቆስ በለሊት ሲገባ፣ ከቁይ ወደ የቦቅላ መጥቶ የነበረው ኃይል ተመልሶ ቁይ መግባት አልችል ብሎ እየተቁለጨለጨ ይገኛል።

የደብረ ዘይትን ህዝብ በየቤቱ እየዞረ ሀብት ንብረታቸውን ሲያቃጥል የነበረ ወንበዴ አውዳሚ ቡድን ማርቆስ ላይ ያለው ቅሪት አካል መጎዳቱን በሰማ ጊዜ ከተኛበት ምሽግ ተነስቶ ማርቆስ ገባ።ገና አባይን ትሻገራለህ!!!

በማታው ምት እስካሁን የተረጋገጠ ስድስት (6 ) እስከመጨረሻው የተሸኘ ሁለት (2) የቆሰለ ነው ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ መ/ር ታደገ ይሁኔ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ተናግሯል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

Ethio 251 Media

18 Nov, 10:11


ይሄ ዛሬ በሙሴባንብ ቀበሌ የተፈፀመ የአንድ ሰው ጀብድ ነው!

ሙሴባንብ - በሚሊሻ ላይ እርምጃ ተወስዷል !!

የግለሰብን ትጥቅ ሊያስፈቱ የሄዱ ሚሊሻዎች ተገድለዋል !!

በታች አርማጭሆ ወረዳ በሙሴባንብ ቀበሌ የአንድን ግለሰብ የግል ጦር መሳሪያ ሊያስወርዱ የሄዱ 3 የሚሊሻ አባላት እርምጃ ተወስዶባቸዋል።

በዛሬዉ ዕለት ህዳር 9 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 1 ሰዓት አካባቢ የአገዛዙን ተልዕኮ ተቀብለዉ በሙሴባንብ ቀበሌ ነዋሪ የሆነዉን አንድን ግለሰብ ከፋኖ ጋር ግንኙነት አለህ በሚል ትጥቁን ለማስፈታት ቤቱን ይከቡትና እጁን እንዲሰጥና የጦር መሳሪያዉን እንዲያወርድ ይጠይቁታል።

በዚህ ጊዜ ግለሰቡ በገዛ ንብረቴ የገዛሁት መሳሪያየ ነዉ ከፈለጋችሁ ገድላችሁ ዉሰዱ እኔ ግን በህይወት እያለሁ ትጥቄን ፈትቸ አልሰጣችሁም ማለቱን ተከትሎ ሚሊሻዎች የግለሰቡን ቤት በጥይት መደብደብ ይጀምራሉ።

በዚህ የተበሳጨዉ ግለሰቡ ትጥቄን ፈትቼ ታሪክ ከማበላሽ ገጥሜ ብሞት ይሻለኛል በማለት ብቻዉን የከበቡትን የሚሊሻ አባላት ገጥሞ ሶስቱንም ባንዳ ሚሊሻዎች (ቅጥረኛ ነፍሰ ገዳዮች) ገድሎ ከቤት ወጥቶ ወደ ፋኖ ገብቷል።

በዚህም የታች አርማጭሆ ወረዳ የብልፅግና መዋቅር የግለሰቡን ሚስትና ልጆች አፍኖ መውሰዱን ኢትዮ 251 ሚዲያ ከቦታው ሰምታለች።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

18 Nov, 09:52


የአማራ ፋኖ በጎጃም የተፈራ ዳምጤ ክፍለጦር የደጋ ዳሞት ብርጌድ ነፃ ባወጣቸው ቀጠናዎች ህዝባዊ ውይይቶችን እያደረገ ይገኛል።

በቀጠናው ወጣቱንና አጠቃላይ ማህበረሰቡን በማቀናጀት ጠላት መከላከል የሚያስችል መዋቅር እየተዘረጋ መሆኑም ተጠቅሷል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ደጋ ዳሞት ብርጌድ ቀጠናዊ ትስስር ኃላፊ ፋኖ ቻላቸው መኮንን ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ያደረገው ቆይታ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ደርሷል ።

ተከታተሉት ...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

18 Nov, 09:30


የአማራ በወሎ የሃውጃኖ ክፍለ ጦር በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ከማህበረሰብ ጋር ውይይት እያደረገ አደረጃጀቶችን እየዘረጋ ይገኛል።

በቀጠናው ሕዝቡን የሚያስተዳድሩ የጎበዝ አለቃዎች በሕዝቡ ተመርጠው ቃለ-መሃላ መፈፀማቸው ተውቋል።

የኢትዮ 251 ዘጋቢ ከወሎ ያደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር አቅርቦታል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

18 Nov, 09:16


የብልፅግናው አገዛዝ በታንክ አጅቦ ፣ህዝብ አስገድዶ የሚያደርጋቸው የአዳራሽ ቅስቀሳዎች በሁሉም ቀጠና እየከሸፈበት ይገኛል።

ከቆቦና ወልደያ ከተማ ኦራሎችን ሰብስቦ የብልፅግና ሆድ አደር አመራሮችን አጅቦ ወደ ሮቢት ከተማ ሲገባ በካላኮርማ ክፍለ ጦር በተወሰደበት እርምጃ ሙትና ቁስለኛ መሆኑ ታውቋል።

የአማራ ፋኖ በወሎ የካላኮርማ ክፍለጦር ዋና አዛዥ ፋኖ ዘውዱ ዳርጌ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

18 Nov, 08:50


በገዛ ወገናቸው ላይ ጦር ሲያዘምቱ ፤ ለጠላት መረጃ ሲሰጡ የተገኙ ባንዳዎች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በከፍተኛ ተጋድሎ ድል ማስመዝገቡ ተገልጿል።

በሸዋ ቀጠና ሁለቱ ዕዞች በጋራ በሚፈፅሟቸው ተጋድሎዎች የአገዛዙ ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሳቸው ታውቋል

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ንጋቱ ይታፈሩ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

18 Nov, 08:38


የብልፅግናው አገዛዝ የፕሮፖጋንዳ ክሽፈት ውስጥ እንደሚገኝ ተገለፀ።

በተለይ በተለያዩ የስርዓቱ በይነ-መረቦች የሚያሰራጫቸው ፋኖን የማይወክሉ ፕሮፖጋንዳዎች በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንደሌላቸው ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ለሲቪክና መንግስታዊ ተቋማት በቂ ጥበቃና ከለላ እየሰጠም ይገኛል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የፅ/ቤት ኃላፊ እና እና የአማራ ፋኖ በጎጃ የገረመው ወንድአወክ ብርጌድ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ ፋኖ በለጠ አብርሃም ከተቋማት ጋር ያደረጉት ቆይታ።

ተከታተሉት .....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

18 Nov, 08:24


የአማራ ፋኖ በጎጃም የበላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር የዛምበረሃ ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አባይነህ ምህረቱ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

18 Nov, 08:00


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሳምነው ፅጌ ብርጌድ በፋኖ ድፋባቸው ሀብታምዬ የሚመራው የታደለ ጠና ሻለቃ በሚያስተዳድራቸው አካባቢዎች ህብረተሰቡን በማስተባበር ከትጥቅ ትግሉ ጎን ለጎን የማህበራዊ አገልግሎቶች እየሰጠ እና የመደራጀት አቅሙን ከፍ የሚያደርጉ ስራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ ተገለፀ።

አራሽ፣ ቀዳሽ፣ዱዓ አድራሽ፣ ተኳሽ ተብሎ የተዘመረለት የአማራ ፋኖ ከገጠመው የህልውና የትጥቅ ትግል ባሻገር ሁሉንም አባላቱን በማስተባበር በራሱና በህብረተሰቡ ጥረት የተለያዩ ገቢ የሚያስገኙ ስራዎችን በማከናወን እራሱን እያደራጀ፣እያስታጠቀ፣ እያሰለጠነ ይገኛል።

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በደራ ጉንዶ መስቀል አካባቢ የሚንቀሳቀሰው የአሳምነው ፅጌ ብርጌድ ታደለ ጠና ሻለቃ በአካባቢው የማገኙትን ሰፋፊ ለም የእርሻ መሬቶችን በኮንትራት የሚሰጡ ማሳዎችን ኮንትራት በመያዝ የጤፍ ምርቱን ያለምንም ብክነት አስገብቷል። ፋኖ እራሱን የሚያደራጀው በዝሕ መልኩ በመሆኑ በተለያዩ አካባቢ ላሉ የፋኖ አደረጃጀቶች ትልቅ ተሞክሮ የሚሆን ስራን እያከናወኑ መሆናቸውም ተነስቷል።

በመጨረሻም ሁሉም የአማራ አደረጃጀቶች ለሸዋ ደራ አማራ ትኩረት እንዲሰጡ በአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ስም እንጠይቃለን ሲል አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል መምህር ፋኖ ይድነቃቸው ማሙዬ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በበላከው መረጃ ገልጿል።

  ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት  !
      
https://t.me/ethio251media
     

Ethio 251 Media

18 Nov, 07:39


የአብነት ተማሪዎች በአገዛዙ ኃይል ከፍተኛ በደል እየተፈፀመባቸው እየተሳደዱ መሆኑ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም 5ኛ ክፍለ ጦር የሕዝብ ግንኙነት ፋኖ ደሳለው ሙሉጌታ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Nov, 20:17


ሰበር ዜና!

በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ጀግናው ፊትአውራሪ አስማረ ዳኜ ብርጌድ ተወርዋሪ የፋኖ አባላት በትላንትናው ዕለት ሌሊት ጊና አገር ከተማ በሁለት አቅጣጫ ሰርገው በመግባት በፈፀሙት የደፈጣ ጥቃት በአሳግርት ወረዳ በሚሊሻ ጠርናፊነት የወረዳውን ህዝብ ሲገድልና ሲያስገድል ፤ ፋኖዎች የሚገኙበትን ቦታ በመሠለል ለማስገድል የባንዳነቱን ተግባር ሲፈፅም የነበረው የአሳግርት/ጊና አገር/ ወረዳ የሚኒሻ ጽ/ቤት ኃላፊ ሀምሳ አለቃ አስናቀ ወንድማገኝ በተወሰደበት እርምጃ እስከ ወዲያኛው ተሸኝቷል።

ባንዳው የሚሊሻ ጠርናፊ ሀምሳ አለቃ አስናቀ በተደጋጋሚ ከጥፋት ድርጊቱ እንዲመለስ ቢጠየቅም የአገዛዙን ወታደር ተማምኖ አሻፈረኝ በማለቱ መኖሪያ ቤቱ  ድረስ በመሄድ በአስማረ ዳኜ ብርጌድ ተወርዋሪ የፋኖ አባላት በተኛበት የማያዳግም እርምጃ ተወስዶበት እስከ ወዲያኛው ተሸኝቷል ሲሉ የኢትዮ 251 ሚዲያ የመረጃ ምንጮች ገልጸዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Nov, 17:27


ህዳር 8/2017 ዓ.ም የአማራ ፋኖ በጎጃም ተጋድሎ
~~

የ7ኛ ( ሀዲስ አለማየሁ) ክ/ጦር #ተድላ ጓሉ ብርጌድ 2ኛ ሻለቃ በአነደድ ወረዳ #ጉዳልማ ቀበሌ አትናውዝ ሜዳ ላይ የብርሃኑ ጁላን ቱልቱላ ሰራዊት ከበባ ውስጥ በማስገናት እያስለፈለፈ ሲቀጠቅጠው ውሏል።
እስካሁን ባለን ተጨባጭ መረጃ 15 ሙት 11 ቁስለኛ ማድረግ ችለዋል።

ሶስት ክላሸንኮቭ
ሁለት የጠላያት ኃይል
ከ500 በላይ የብሬል ተተኳሽ ማርከዋል።

በሌላ አውደ ውጊያ የ2ኛ(የተፈራ ዳምጤ) ክፍለ ጦር
1. መዝገቡ ዋለልኝ ብርጌድ
አለማየሁ ሁነኛው ሻለቃ
ጌታቸው በጋሻው ሻለቃ
አጃነው አሞኘ ሻለቃ
ተጠባባቂ ባይሌ አዱኛ ሻለቃ
2. ደጋ ዳሞት ብርጌድ 3ኛ ሻለቃ
3. መብረቁ ብርጌድ 1ኛ ሻለቃ
በጥምረት በቢቡኝ ወረዳ ወይን ውሃ ከተማ ላይ ከቦ የሚገኘውን የአብይ አህመድን ጭፍጫፊ ቡድን ሌሊት 1:00 ጀምሮ እንደፈልፈል አፈር ውስጥ ቢገባም ልኩን ሲያገኝ ውሏል።

በውጊያው 46 ሙት 29 ቁስለኛ ማድረግ ተችሏል።
ሁለት የጠላት ኃይል
ሁለት ክላሸንኮቭ መሳሪያ ከነሙሉ ትጥቅ እንዲሁም
90 ጥይት ተማርኳል።

አስቀያሚው ነገር ወይን ውሃ ከተማ ውስጥ ያለው ጠላት በፋሲለ ድስ ቤተ-ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ ነው መሽጎ የሚገኘው።
ወይን ውሃ ለ4:00 ያክል በፋኖ እጅ ገብታ ነበር።

ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ
የአማራ ፋኖ በጎጃም ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ምክትል ኃላፊ

Ethio 251 Media

17 Nov, 16:13


ወንድማማቾቹ የሸዋ እዞች በጥምረት የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ ድል ተቀዳጁ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝና የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በደብረ ብርሀን ከተማ ዙሪያ ባደረጉት ተጋድሎ ከፍተኛ ድል አስመዝግበዋል።

በደረቁ ሌሊት መነሻውን ደብረ ብርሀን ከተማ አድርጎ የፋኖን ሀይል በከበባ ለማጥቃት ያሰበው  እነዚህ የአገዛዙ ጥምር ሀይሎች ያሰቡት ሳይሳካ በወንድማማቾቹ የሸዋ ዕዞች በከፍተኛ ሁኔታ እንዲመታ ተደርጓል።

ሁለቱ ወንድማማች እዞች ባደረጉት ተጋድሎ የመከላከያ፣ አድማ ብተናና የሚሊሻ ሀይሎቹ በጥምረት በደብረ ብርሀን አቅራቢያ ቀይት ዙሪያ ጭራሮ ደብርና ባቄሎ በሚባሉት አካባቢዎች ላይ አዳሩን ሲክብ ያደረውን ምሽግ ሰብረው ድልን ተቀዳጅተዋል።

ይህ በአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝና አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ ብርቱ ጥምር ክንድ የተመታው የአገዛዙ ጥምር ሀይልም በደረሰበት ምት በአካባቢው ያሉ የንፁሀን ሀብትና ንብረቶችን እያወደመና መኖሪያ ቤቶችን እያቃጠለ አካባቢውን ለቅቆ መውጣቱን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ የመሀመድ ቢሆነኝ ክፍለጦር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ምናሉ ከበደ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

የውጊያ ሂደቱን ለጣቢያችን የገለጠው ፋኖ ምናሉ የሁለቱ እዞች ሰራዊት ባደረገው ትንቅንቅና ባገኘው ድል ከትንቅንቅ እስከ ድል በደስታ ታጅቦ ጠላትን ገርፎታል ብሏል።

ሁለቱ እዞች በትናንትናው እለት በታሪካዊቷ አንኮበር ከተማ በጋራ ባደረጉት ተጋድሎና በጠላት ላይ በወሰዱት እርምጃ ከፍተኛ ድል መቀዳጀታቸውን የአማራ ፋኖ ሸዋ እዝ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ንጋቱ ይታፈሩ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ያደረሰውን ዘገባ ማድረሳችን ይታወሳል።

የሁለቱ እዞች የጋራ ጥምረትና ተጋድሎም አሁን ላይ በቀጣናው የገባውንና አገዛዙ ኤሊት ፎርስ እያለ የሚጠራውን ሀይል እስከ ተላላኪ ሚሊሻና አድማብተናው እየመታ ከፍተኛ ድል እየተቀዳጁበት እንደሆነም የህዝብ ግንኙነት ክፍሎቹ ባደረሱት መረጃ ጠቁመዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Nov, 15:58


📌ጥብቅ መረጃ!

ምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ እና ባንዳው አረጋ ከበደ የመሩት ስብሰባ እና ግምገማ መጠናቀቁ ታውቋል። ተሰብሳቢዎች የእዝ መሪ ጀነራሎች ሲሆኑ ብርሃኑ ጁላ የሚከተሉትን ውሳኔዎች በግልፅ አስቀምጧል።

1) እስከ ታህሳስ 30- 2017 አም ጦርነቱን ማጠናቀቅ ካልተቻለ መከላከያውን እናስወጣለን የሚል የውሳኔ ሃሳብ በግልፅ አስቀምጧል።

2) ማሸነፍ ያልቻልነው በአረጋ አመራሮች ምክንያት ስለሆነ አረጋ አመራርህ ላይ እርምጃ ውሰድ የሚል ጥብቅ መመሪያ ሰጧል።

3) አንድ ኮር ከወለጋ ተንቀሳቅሶ ወሎና ጎጃም እንደሚሰፍርም ውሳኔው ተነግሯቸዋል።

በመጨረሻም ምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ እነ አረጋ ከበደን መንግስት ከዚህ በላይ ሊዋጋላችሁ አይችልም:: እንደ ብልፅግና ከጎናችን ቁማችሁ መታገል ካልቻላችሁ የክልሉን ስልጣን ለፋኖ አስረክቡትና ከወላዋዮች ከእናንተ ይልቅ በግልፅ አቋም ካላቸው ከእነሱ ጋር አጋር ብንሆን ይሻላል ሲል ተደምጧል።

ለኢትዮ 251 ሚዲያ መረጃውን ያደረሱ ምንጮች ምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ግን ምን እንዳጨሰ ባናውቅም በመጨረሻ ያነሳው ሀሳብ ግን አስቆናል ብለዋል።

ኢትዮ 251ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Nov, 15:47


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ የጊራናው ባለ ሽርጡ ክፍለጦር ታላቅ ድል ተጎናፀፈ::

በፋኖ እንድሪስ ጉድሌ የሚመራው የጊራናው ባለ ሽርጡ ክፍለጦር መነሻዉን መርሳ ከተማ አድርጎ ወርጌሳ ከተማን ለመቆጣጠር አሰፍሰፎ የመጣዉን የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ጦር ኒኒ በር ላይ ከበባ በማድረግ አይቀጡ ቅጣት ቀጥተዉ መልሰዉታል።

ጨፍጫፊዉ ሰርዓት በመካናይዝድ የታገዘ ማጥቃት ለመፈፀም ቢሞክርም ክንደ ብርቱዎቹ የፋኖ እንድሪስ ጉድሌ ልጆችን በትር መቋቋም ባለመቻሉ ሙትና ቁሰለኛዉን እያንጠባጠበ ማሸላ ለማሸላ እግሬ አዉጭኝ ብሎ ፈርጥጧል ።

የህልዉና ተጋፍሎው እስከ ድልና ነፃነት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Nov, 14:39


ሰበር ዜና!

በደብረብርሃን ከተማ አስተዳደር ጠባሴ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው አንጎለላ (ሰሚነሽ) የብልፅግናው ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ተሰነዘረ።

በኢ/ር ደሳለኝ ሲያስብ ሸዋ ዋና መሪነት በፊትአውራሪ ኢ/ር ባዩ አለባቸው ዋና ጦር አዛዥነት የሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ነጎድጓድ ክፍለጦር አንበሳው ብርጌድ አርበኛ አሊ ሻለቃና ገበዬሁ ሻለቃ አንጎለላ(ሰሚነሽ ኪዳነምህረት) በሚገኘው የብልፅግናው አራዊት ሰራዊት ዛሬ ህዳር 8/2017 ዓ.ም ከምሽቱቱ 5:00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 8:00 ሰዓት በሰነዘረ መብረቃዊ ጥቃት የአማራን ህዝብ ለማጥፋት ተከማችቶ የነበረው ኃይል ካምፑን ለቆ ለመበታተን ተገዷል።

በተሰነዘረው ጥቃትም በጠላት ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረስ ይቻላል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ መነሻውን ደብረብርሃን ከተማ መድረሻውን ከደብረብርሃን ከተማ 5ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ በሚገኘው ባሶና ወራና ወረዳ ጭራሮ ደብር ቀበሌ ያደረገ የአገዛዙ ዙፋን አስጠባቂ መከላከያ፣ አድማ በታኝና ሚሊሻ አባላት ላይ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ አንበሳው ብርጌድ አባላት በድንቅ ወታደራዊ ብቃት በመመታቱ ከደብረብርሃን ከተማ ተጨማሪ ኃይል ሲያስጠጋ መሀል አምባና ዙሪያው ይንቀሳቀስ የነበረው በጀግናው አርበኛ "መሀመድ ቢሆነኝ" ስም የተሰየመው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ክፍለጦር ራንቦ ብርጌድ አባላት ለአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ወንድሞቾቻቸው እንደ አቦሸማኔ ተወርውረው በመድረስ በቅንጅት በጠላት ላይ በሰነዘሩት ምት ተደናግጦ ወደ ደብረብርሃን ለመፈርጠጥ ተገዷል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃ ገልጿል።

ኢትዮ 251ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 12:33


የአማራ ፋኖ ከግንባር ተጋድሎ ባሻገር የሚከውናቸው ማህበራዊ ተሳትፎዎች ቀጥለዋል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር ሃይለማርያም ማሞ ብርጌድ ከተጋድሎ ባሻገር በማህበራዊ አገልግሎት ዘርፍ አንደኛው የሆነውን የአርሶ አደሩን ሰብል በመሰብሰብ የህዝብ ልጅነትን የወገን አጋርነትን በተግባር ማሳየታቸው ተገልጿል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 12:15


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ  በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች የሁሉም እምነቶች ኃይማኖታዊ ክብረ በዓሎች በሰላም እንዲከበሩ  በቂ ጥበቃና የፀጥታ ማስከበር ስራ እያከናወነ መሆኑ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አርበኛ ምንተስኖት ወንድአፈረው ክብረ በዓሉን ለታደሙት ምዕመናን መልዕክት አስተላልፈዋል ። 

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 11:55


የአማራ ፋኖ በጎጃም የበላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አዳዲስ ኮማንዶዎችን አሰልጥኖ አስመረቀ።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የአማራ ፋኖ በጎጃም የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ አበበ ሰው መሆንን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።

ለኢትዮ 251 የደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አባቡ አቅርቦታል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 11:40


የአማራ ፋኖ በጎጃም የፀረ- ተሽከርካሪ መሳሪያ ሰርቶ ጥቅም ላይ ማዋሉ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ዋና ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሴ በሙከራ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ለቴክኖሎጂው ፈጠራ ውጤት ሲተጉ ለነበሩ ወጣት ሙህራኖችን ማበረታቻ መስጠታቸውም ታውቋል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 11:25


ጥንታዊው የዲማ ጊዮርጊስ ገዳም በአገዛዙ የድሮን ጥቃትና የከባድ መሳሪያ ድብደባ እንዲወድም ተደርጓል።

የሐዲስ አለማየሁ ሙዚየምን ጨምሮ በርካታ ቅርሶች መውደማቸውም ታውቋል።

ከአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ ክፍለጦር ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን የምስል ማስረጃ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አባቡ አቅርቦታል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 10:54


አረመኔው የአብይ አህመድ ብልፅግና በሸዋ መንዝ ቀጠና ባሽ ስደተኛ መጠለያ ካምፕ ላይ ባደረሰው ጥቃት የተገደሉ እናትና ልጅ !

ኢትዮ 251 ሚዲያ

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 10:48


በጎጃም ቀጠና ባሉ አደረጃጀቶ ከመነሻው ጀምሮ አሁን የደረሰበት ደረጃና የትግል ውጤቱ ምን ይመስላል ?

የአማራ ፋኖ በጎጃም የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ ፋኖ እሸቱ ጌትነት ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ዘለግ ያለ ቆይታ በሁለት ክፍል አድርጓል።

ክፍል 2

ተከታተሉት ......

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 10:22


የአማራ ፋኖ በወሎ  ሃውጃኖ ክፍለ ጦር የአስተዳደር መምሪያ ኃላፊ የሆነው ፋኖ ሃይሉ ማርዬ በክፍለ ጦሩ ከተደራጁ አባት አርበኞች ጋር ያደረገው ቆይታ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ደርሷታል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 10:09


በሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ ቃሊም ላይ የተፈፀመው የድሮን ጥቃት በንፁኃን ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

በመኖሪያ ቤት ላይ የተፈፀመው የድሮን ጥቃት የንፁኻንን ህይወት ቀጥፏል።

ተከታተሉት......

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 09:55


የአማራ ፋኖ በወሎ የጊራናው ባለሽርጡ ክፍለ ጦር በመርሳ ሀብሩ ወረዳ ሊብሶ ከተማ ላይ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል።

በተመሳሳይ በወልድያ መስመር ቃሊም መገንጠያ አፍቄራ በተባለ ቦታ የዞብል አምባ ክፍለጦር እና አሳምነው ክፍለ ጦር በጠላት ኃይል ላይ በወሰዱት የደፈጣ ጥቃት ሙትና ቁስለኛ አድርገውታል።

የአማራ ፋኖ በወሎ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አበበ ሙላት በግንባር ተጋድሎና የድል ውጤቶች ዙሪያ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 09:42


በጎንደር የተሰማሩት የብልፅግና ደህንነቶች!

የጎንደር ከተማ ወጣቶችን እየሰለሉ ለአረመኔው የብልፅግና አገዛዝ አሳልፈው በመስጠት የባንዳነት ተግባርን እየፈፀሙ ከሚገኙት መካከል ሞላ ጥላሁን የተባለ ደህንነት አንዱ እንደሆነ ለኢትዮ 251 ሚዲያ መረጃው ደርሷል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 09:30


በባህርዳርና በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ወጣቶችና እያሳፈሱ የሚገኙት የብልፅግና ካድሬዎች

1. ደስዬ ደጀን - የክልሉ ፀጥታና ቢሮ ኃላፊ
2. ዶ/ር እሸቱ -የሰላምና ደህንነችት ቢሮ ም/ኃላፊ
3. ኮማንደር ክንዱ - የምርመራ ምክትል ኃላፊ
4. ኮሚሽነር እንየው - የወንጀል መከላከል ኃላፊ
5. አቶ ገደቤ - የሚሊሻ ምክትል ኃላፊ

የአማራን ወጣት እየታፈሰ እንዲገደል የሚያደርጉ የክልሉ የፀጥታ አመራሮች መሆናቸውን ለኢትዮ 251 ሚዲያ ደርሷታል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

14 Nov, 09:21


በተፈናቃይ ካምፕ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት በርካቶች ተገደሉ !

ኢትዮ 251 ሚዲያ ህዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም

በዛሬው እለት ህዳር 5 ቀን 2017 ዓም መንዝ ማማ ባሽ ንዑስ ወረዳ ላይ በተፈናቃይ ካምፕ ላይ አገዛዙ በፈፀመው የድሮን ጥቃት በርካቶች የህይወትና የአካል ጉዳት ደረሰባቸው።

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ማማ ወረዳ በ ባሽ ንዑስ ወረዳ የሚገኘው ከኦሮሚያ ክልል ተፈናቃይ አማራዎች ካምፕ ላይ በተፈፀመው ዘግናኝ ጥቃት 5 ሰዎች ሲሞቱ 7 ሰዎች ደግሞ ከባድና ቀላል ቁስለኛ እንዲሆኑ ማድረጉን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት እዝ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

በሽመልስ አብዲሳ ኦነጋዊ አገዛዝ ተፈናቅለው በቀበሌ ሼድ ውስጥ የተጠለሉ አማራዎችን በድሮን ጥቃት መምታቱ ተሰምቷል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

13 Nov, 16:21


https://youtube.com/live/y-LgOUpRSUw?feature=share

Ethio 251 Media

13 Nov, 15:37


ሰበር ዜና!

የአገዛዙ ሰራዊት 11 ሙትና 12 ቁስለኛ ሁኗል!

በህዳር 4/2017 ዓ. ም የአማራ ፋኖ በጎጃም ቢትወደድ አያሌው መኮነን ብርጌድ ቀኝ አዝማች ባያብል ደስታ ሻለቃ በሰሜን አቸፈር ወረዳ ለግዲያ ቀበሌ ላይ የጠላትን ኃይል በደፈጣ በመያዝ 11 ሙትና 12 ቁስለኛ ማድረግ ችሏል። ውጊያው የጠላት ኃይል ከባህር ዳር ወደ ቁንዝላ በማቅናት ሬሽን አድርሶ ሲመለስ ነው ጀግኖቹ የቢትወደድ አያሌው ልጆች ጠላትን መብረቃዊ ጥቃት የፈጸሙት።
የቢትወደድ አያሌው ልጆች በቅርቡ እትየ ምንትዋብ ት/ቤት፣ባድማ አካባቢ የነበረውንና ሰንቀጣ ተራራ ላይ የነበረውን የአብይ ጭፍራ ሰራዊት ልኩን በማሳየት ቀጠናውን ነጻ ማድረግ ችለዋል።

በዚህ የተበሳጨው የአብይ ገዳይ ቡድን በእስቱሙት ቀበሌ ካንቻየ ከተማ የንጹሃንን ንብረት ሲዘርፍና ሲያወድም ውሏል። በተለይ የአንድን አርሶ አደር 13 ኩንታል ጤፍ ዘርፈዋል።

በሌላ በኩል 15 የመከላከያ አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ከጅጋ ከተማ ወጥተው ፋኖን ተቀላቅለዋል።

የተቀላቀሉት ወደ 5ኛ ክፍለ ጦር አረንዛው ዳሞት ብርጌድ ጅጋ ሻለቃ ነው። ዛሬ ፋኖን የተቀላቀሉት የመከላከያ አባላት የሚደረገው ውጊያ ለሃገር ግንባታ (ህልውና) ሳይሆን አብይ ለስልጣኑ ብቻ መሆኑን የአማራ ፋኖ በጎጃም ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ምክትል ኃላፊ ፋኖ ዮሐንስ አለማየሁ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

13 Nov, 15:02


ጥንታዊው ዲማ ጊዮርጊስ ገዳም በአገዛዙ ከባድ መሳሪያና እሳት እንዲወድም ተደረገ !

ኢትዮ 251 ሚዲያ ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም

ወደ እነማይ ወረዳ ያቀናው የአገዛዙ ሀይል በስፍራው በፋኖ ሀይሎች ከፍተኛ ምት ደርሶበታል። ይህ ያመመው የአገዛዙ ሀይልም በወረዳው የሚገኘውን የዲማ ጊዮርጊስ ገደም የሚገኘውን የፍቅር እስከ መቃብር ፊልም የተሰራበትን የጥንት አባቶቻችንን ታሪክ የሚዘክረውን የአዲስ አለማየሁ ሙዚዬም ከነ ሙሉ ጥንታዊ ቅርሶቹ ሳይቀር አቃጥሎ መሄዱን
የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ የበላይ ዘለቀ ክፍለጦር ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

በዲማ ጊዮርጊስ እና በደብረ ፅሞና ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ነጋዴዎችን፣ የሹፌሮችን ሀብት ንብረት ባጃጎችን፣ ሲኖትራክና ሌሎች በርካታ ሀብትና ንብረቶችን ዘርፈዋል ውድመቶችንም አድርገዋል።

የአገዛዙ ሀይሎች በዲማ ጊዮርጊስ ሸቀጣ ሸቀጥ ይነግዱ የነበሩ ነጋዴዎች ሱቅ በሙሉ ዘርፈዋፎል፣ በዲማ ጊዮርጊስስ የአብቁተ ቅርጫፍን ዘርፎና አውድሟል፣ በዲማ ጊዮርጊስ ነዋሪዎችን ቤት እየሰበረ የቤት እቃዎችን ወደ ቢቸና ከተማ ጭኖም ወስዷል።

ዘራፌው የአብይ አህመድ ቅጥረኛ ቡድን በደብረ ፅሞና ቀበሌ የአምዕሮ ህሙማን የነበር አንድ ግለሰብ፣ በታላቁ ዲማ ጊዮርጊስ ነዋሪ የሆኑት አንድ ካሀን እና አራት ንፁሀንን አገዛዙ ረሽኖ ሄዷል ተብሏል።

ራሱን እንደ መንግስት የሚቆጥረው የአብይ አህመድ ሽብርተኛ ቡድን በእነማይ ወረዳ ዲማ ጊዮርጊስ ነዋሪዎች ላይ የፈፀመውን ነውረኛ ተግባር እንዲህ በምስል በሚታየው መልኩ አውድሞና ፀረ አማራነቱን አሳይቶ ወደ ቢቸና ከተማ መሄዱን ከአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ይበልጣል ጌቴ ኔኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

13 Nov, 13:29


በወሎ ቀጠና ተጋድሎዎች ቀጥለዋል።

በአማራ ፋኖ በወሎ የተማረኩት የአገዛዙ ሠራዊት አባላት ፤  የምርኮኛ አያያዝና ጥበቃ በጦር ጠበብቶቹ ኮሎኔሎች በአግባቡ እየተመራ ይገኛል።

የአማራ ፋኖ በወሎ ከፍተኛ አመራሮች ኮሎኔል ፋኖ ሞገስ ዘገየ እና ኮሎኔል ፈንታሁን መኩዬ ከ48ኛ ክፍለጦር የምርኮኛ አባላት ጋር ቆይታ አድርገዋል።

የኢትዮ 251 ዘጋቢ ከግንባር ያደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር አቅርቦታል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

11 Nov, 11:18


ሰበር ዜና

የቅጥረኛ ሚሊሻ ሰብልን "ህዝብ አስገድጀ አሳጭዳለሁ" ብሎ የተንቀሳቀሰው ወራሪው የገዳዩ ቡድን ሠራዊት በአናብስቶቹ በተወሰደበት እርምጃ  "የሚሊሻ አስክሬን በሸራ ጠቅልሎ" መመለሱ ተገለፀ !

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ ሚዳ ወረዳ መሽጎ የነበረው ራሱን የመከላከያ ሰራዊት ብሎ የሚጠራው የሰው በላው ስብስብ በዛሬው ዕለት በአርበኛ መከታው ማሞ ልጆች ሲገረፍ ማርፈዱን ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመላክታል።

በዛሬው ዕለት ህዳር 02/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:00 ላይ የባንዳውን የሚሊሻ ሰብል "ህዝብን አስገድጄ እሰበስባለሁ!" በሚል መነሻውን መራኛ ከተማ አድርጎ ወደ ሶርች ቀበሌ በጠዋቱ የተጓዘው የሰው በላው ስብስብ በተወሰደበት እርምጃ የባንዳውን የሚሊሻ አስክሬን በሸራ ጠቅሎ ጭኖ መመለሱ ተገልጿል።

ይህን አስደናቂ ኦፕሬሽን በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አስማረ ዳኜ ብርጌድ በፋኖ ሻምበል በየነ የሚመራው አንበሳው ሻለቃ ( ሻለቃ 1 ) የተሰራ ልዩ ሰርጅካል ኦፕሬሽን ሲሆን፤ እንደ ተርብ የሚናደፉት ሸማቂዎቹ ጠላት ያሰበውን ሳያሳካ የባንዳውን የሚሊሸ አስክሬን ታቅፎ እንዲመለስ አድርገውታል።

የአናብስቶቹን ክንድ መቋቋም ያቃተው የሰው በላው ስብስብ የሶርች ቀበሌ የአርሶ አደሩን የደረሰ ሰብል ሞርተር፣ ዙ-23 እና ዲሽቃ በመተኮስ እንዲቃጠል ማድረጉንም የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢትዮ 251 ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

11 Nov, 09:21


ቅምሻ
ከፋኖ ኮሎኔሎች ጋር…
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 20:55


ሰበር ዜና!

እነማይ ጎጃም አማራ

የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር ህዳር 01 ቀን 2017 ዓ.ም በእነማይ ወርዳ ዲማ ጊዮረጊስ ከባድ ውጊያ ሲያካሂድ ውሏል።

በእነማይ ወርዳ ዲማ ጊዮረጊስ በትላንትነው እለት እየተካሄደ ባለው ውጊያ ልዮ የሚያደርገው ጥቅምት 29/2017ዓም የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር አባ ኮስትር ብርጌድ ልዮ ኮማንዶው የተመረቀው የጠላት ሀይል ሲያራግፈው ውሏል።

በትላንትነው እለት ጥቅምት 30/2017ዓም የጠላት ሀይል ከሞጣ፣ ከግንደዊን፣ ከደጀን (1) BM107፣ ፔንፔ፣ ሞርተር ጭምር በርካታ ሀይል ይዞ በእነማይ ወርዳ ዲማ ጊዮረጊስ የገባ ቢሆንም ጀግኖቹ የኮስትር ልጆች ጠላትን እንደ ቅጠል ሲያራግፍት ውለዋል።በዚህ ውጊያ በዲማ ጊዮወርጊስ ተራራማ ቦታዎችን ጠላት ይዞ ያደር ቢሆንም ጥቅምት ህዳር 01/2017ዓም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ከደብርወርቅ ከተማ ሁለት አይሲዙ የአገዛዙ ሀይል ይዞ የገባ ቢሆንም ጠላት ሁለት አይሲዙ አስከሬን ይዞ ወደ ደብርወረቅ ከተማ ሄዶል።

በትላንትነው እለት በተካሄደው ውጊያ የአባ ኮስትር ብርጌድ አካል የሆነችው ጠቅል ሻለቃ በእነማይ ወርዳ ማህበር ብርሀን ቀበሌ ከባድ ውጊያ ስታካሂድ ውላለች። ጠቅል ሻለቃ የቢቸና ሚኒሻ፣ ፖሊስ፣ አድማ ብተና ከማህበር ብርሀን ቀበሌ ጀምራ እያሮሯጠች ወደ ቢቸና ከተማ አስገብተዋለች።
ጠቅል ሻለቃ በትላንትነው እለት እያካሄደችው ባለው ውጊያ ከአስር በላይ የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሀይሎችን እስከወዳኜው ሸኝታለች።በዚህ ውጊያ የደጀን ተወላጅ የሆነ አንድ የፖሊስ አባል የነበር ባንዳ ሳጅን ተሾመን ምርኮኛ አድርጋለች።

በትላንትነው እለት ጥቅምት 29/2017ዓም አባ ኮስትር ብርጌድ በዲማ ጊዮርጊ እያካሄደ እንደሆነ መርጃ የደርሰው የበላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር አካል የሆነው ሶማ ብርጌድ ደብርወርቅ ከተማ በመግባት በርካታ የጠላት ሀይል ደምስሷል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር አባ ኮስትር ብርጌድ ህዳር 01/2017ዓም በዲማ ጊዮርጊስ ቤተ መስቀል ባካሄደው የመልሶ ማጥቃት የውጊያ ስልቱን ቀይሮ የበላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ጦር መሪ መቶ አለቃ ውዳለው፣የበላይ ዘለቀ ዘመቻ መሪ አምሳ አለቃ ይወሴፍ ቢያዝን፣የአባ ኮስትር ብርጌድ ጦር መሪ አስር አለቃ ግዛቸው አስናቀ፣ የአባ ኮስትር ብርጌድ ዘመቻ መሪ ዝምተኛው መብረቅ ሀምሳ አለቃ ፋኖ ኮማንዶ መንበር አደም እንዲሁም የአባ ኮስትር ብርጌድ ልዮ ኮማንዶ መሪ ኮማንዶ የፀደው በየነ በጋራ ባደረጉት እልህ አስጨራሽ ውጊያ አባ ኮስትር ብርጌድ በዛሬው እለት ድል በድል ሆኖል።

በዛሬው እለት ህዳር 01/2017ዓም በብርቅየ የአባ ኮስትር ብርጌድ ልዮ ኮማንዶዎች የትላንቱ ሙሽራዎች የዛሬው ሚሳኤሎች ባደርጉት ውጊያ ከ50 በላይ የጠላት ሀይል ሲደመስሱ ከ20 በላይ የጠላት ሀይል ከባድ እና ቀላል ቁስለኛ አድርገዋል። በአባ ኮስትር ብርጌድ ልዮ ኮማንዶ 10 የመከላከያ አባል እንዲሁም 3 አድማ ብተና ማርከዋል።

በዛሬው እለት በተካሄደው ውጊያ የበላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ስር የሚገኜው ደበይ ጮቄ ብርጌድ እና የበላይ ዘለቀ ክፍለ 8ኛ ጦር እስፔሻል ፎርስ በጋራ በመሆን በእነማይ ወርዳ መንግስቶ ቀበሌ መሌ ጎጥ ላይ በመሆን ወደ ዲማ ጊዮወርጊስ የሚሄደውን የጠላት ሀይል ሲረፈርፍት ውለዋል።ዘራፌ እና ፀር አማራ የሆነው የብርሀኑ ጁላ ሰራዊት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሀይማኖት የሆነችው ቤተክርስትያን በታላቁ ዲማ ጊዮወርጊስ ገዳም ላይ የአገዛዙ ሀይል BM107፣ ዙ23፣ፔንፔ፣ሞርተር ሲወርውር ውሏል።የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሀይል በዲማ ጊዮወረጊስ የግለሰብ ሀብት ንብርቶችን ዘርፎል አውድሟል።

በሌላ የውጊያ ውሎ በአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ስር የሚገኜው ዛንበራ ብርጌድ በአገዛዙ ሀይል ደጀን ወርዳ ወርቃምባ ቀበሌ ህዝባዊ ስብሰባ የጠራ ቢሆንም ጀግኖቹ የዛንበራ ብርጌድ ፋኖዎች በየናኛት እና ወርቃምባ ቀበሌ ውጊያ በማካሄድ አገዛዙ የጠርውን ህዝባዊ ስብሰባ እንዳይካሄድ አድርገውታል።

መረጃውን የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ይበልጣል ጌቴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 20:35


ዲሲ ሞቅ ሞቅ እያለ ነው።

#AmharaGenocide
#WarOnAmhara

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
 
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 20:35


አሜሪካ ሚኒሶታ ሞቅ ሞቅ እያለ ነው።

#AmharaGenocide
#WarOnAmhara

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
 
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 19:01


ደቡብ አፍሪካዎች!

በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ አማራዎችና የአማራ ትግል ደጋፊ ትውልደ ኢትዮጵያን በአማራ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ሁሉን አቀፍ ጥቃት በሰላማዊ ሰልፍ አውግዘዋል።

#AmharaGenocide
#WarOnAmhara

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
 
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 18:53


ለንደን🙏

#AmharaGenocide
#WarOnAmhara

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
 
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 18:40


የእንግሊዝ አገር አማራዎች በዛሬው ዕለት አገዛዙ በአማራ ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን ግፍና በደል በዚህ መልኩ ድምጻቸውን አሰምተዋል።

ኮርተናል። ተጠናክሮ መቀጠል አለበት!

#AmharaGenocide
#WarOnAmhara

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
 
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 16:57


ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ!

November 16,2024
Sweden, Stockholm city

አዘጋጅ:- በስዊድን የአማራ ማህበር!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
 
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

10 Nov, 16:41


ሰበር ዜና!

ሁለቱ ዕዞች አስደናቂ ድል አስመዘገቡ!

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የጀነራል ነጋ ተገኝ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ሻለቃ ፀዳሉ ደሴ እና የአማራ ፋኖ በጎንደር ሜጄር ጀነራል ውባንተ አባተ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ሻለቃ ተመስገን ውባንተ አባተ የሚመሩት ሁለቱ ክፍለጦሮች ከሃሙስ እለት ጀምሮ እያደረገው ባለው የመደበኛ ውጊያ በአገዛዙ ላይ ከፍተኛ ኪሳራን እያደረሰ ነው።

ሆኖም እንደሚያወቀው ሃሙስ እለት በተደረገው የደፈጣ ጥቃት 13 የፖሊስ አባላትና 7 ሚኒሻዎች በዕለቱ ግባዓተ መሬታቸው ተፈፅሟል። እስከዛሬው ቀን ድረስ የመከላከያው እና የአድማ ብተና አስከሬኖችንም በፓትሮል እያጓጎዘ እንደሚገኝ ኢትዮ 251 ሚዲያ ለማወቅ ችላለች።

የአገዛዙ ሰራዊት ሳያስበው ወደጫካው በፋኖወቹ ተስቦ የገባው የመሐመድ ተሰማ ሰራዊት ከክንደ ብርቱው የአማራ ፋኖ ጎንጀር ዕዝ ስልጠና መምሪያ ኃላፊና በጀነራል ነጋ ክፍለጦር አዛዥ ሻለቃ ፀዳሉ ደሴ እጅ አምልጦ መፈርጠጥ እንዳልቻለ የጀነራል ነጋ ተገኝ ክፍለጦር አሳምነው ብርጌድ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፍቃዴ አምባው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

የጀግናው ሜጀር ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለጦር አናብስት ልጆች ጋር በጥምረት እየተካሄደ ባለው በዚህ ታሪካዊ ተጋድሎ ከአምስት በላይ ዲሽቃ በማሰለፍ መሬት ላይም በተቀበረ ፈንጂ እንዲሁም በሞርታር የታገዘው ውጊያ ለማድረግ ቢሞክርም አገዛዙ ጠላትን ማርበድበድ ተችሏል፤
በዚህም ውጊያ ከእግሬኛ ተዋጊ ውጭ  ከአራት በላይ የዲሽቃ ተኳሾችን አንድ የአስር አለቃ አዛዥን እስከመጨረሻው  መሸኘት ተችሏል፤ አሁንም የብልጽግና ሰራዊት ተከቦ እየተቀጠቀጠ ይገኛል ሲል ፍቃዴ አምባው ለጣቢያችን ገልጿል።

  የጠላትን አስከሬንም ገበሬው በሃዘኔታ እያነሱ በክብር መቅበራቸውን የአይን እማኞች ለጣቢያችን ገልጸዋል።

ከዚህ ባሻገር የባንዳው ጥርቅም ፋኖ ሆኖ ከወጣው የኪንቲ አርሶ አደሮች ውጭ ያገኘውን ሴቶች እና ህፃናትን በመሰብሰብ ትምህርት እናስተምር የሚል ማባበያ ሲናገር ሁሉም እናቶች እና አዛውንቶች ምንም አይነት ትምህርት እንድታስተምሩንም፤ እንድታስተምሩልንም አንፈልግም ሲሉ በቁጣ አሰናብተውታል።

በዚህ መልስ እጅግ የተደናገጠው እና የተበሳጨው የብልጽግናው መከላከያ አመራር አንድ ንፁህ ገበሬን ጥይት ተኩሶ መግደሉን የአይን እማኞች ለጣቢያችን ገልጸዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
 
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 22:17


የድጋፍ አማራጮች !

ኢትዮ 251 ሚዲያን ለመደገፍ አማራጮችን ስትጠይቁን ለነበራችሁ ቤተሰቦቻችን ሁሉ !

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።


Bank Acct Info: Chase Bank
Account number
675535275
Routing number
322271627

Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

09 Nov, 21:16


ጎንደር ጠቅላይ ግዛት
ጥቅምት 30/2017ዓ.ም

ፋርጣ

ለ2 ቀናት የቆዬው ውጊያ ዛሬም ከጠዋቱ ጀምሮ እሥከ ምሽት 1:30 ሙሉ ቀን ውሏል። በ2 ቀናት አውደ ውጊያ የአማራ ፋኖን ክንድ መቋቋም የተሳነው የብርሐኑ ጁላ ሠራዊት በጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጠዋት ከተለያዩ የቀጠናው መዳረሻዎች ወደ ደብረ ታቦር ዙሪያ መጥቷል። የብርሐኑ ጁላ ጦር ከእሥቴ፣ ከአምበሳሜ፣ ከልጫ፣ ከግንዳ ጠመም፣ ከማሕደረ ማርያም፣ ከደብረ ታቦርና ከወረታ ወደ ዓለም በር ቀጠና አቅንቷል። የአቢይ ሸኔ ወምበር ጠባቂ አራዊትት ሠራዊት በሚመጣበት አቅጣጫ ሁሉ በጠዋቱ አሪንጎ አቦ፣ ኪንቲና ዝምሃ የት ነው ሢል ባጅቷል። የወገን ጦር የሀብቴ ወልዴ ጎንደር ዕዝና የባዬ ቀናው አማራ ፋኖ በጎንደር በጥምረት እልህ አሥጨራሽ ውጊያ አድርገዋል። በአርበኛ ፀዳሉ ደሤ የሚመራው ጀነራል ነጋ ተገኝና በአርበኛ ተመሥገን ውባንተ አባተ የሚመራው ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦር በፍጹም አንድነት ጠላትን ሢያምበረክኩ ውለዋል። የወገን ጦር የቡድን መሣሪያዎች ዲሽቃና ሞርተሮች ኢላማቸውን የጠበቁ ውጤቶችን አሥመዝግበዋል። ውጊያ ሢደረግባቸው የዋሉ መዳረሻዎች፦
ኪንቲ፣ አሪንጎ፣ ዝምሃ፣አምባ አገር፣ ጎርጓ፣ ሣጨራ፣ ግብር፣ጣይሩ፣ ቃንዚላ፣ ሾላ ሜዳና የመሣሠሉት ቀበሌዎች ናቸው። እሥከ ምሽቱ 1:30 ድረሥ ውጊያ ተደርጓል። በተፈጥሮ አሥገዳጅ ሁኔታ ውጊያው ተቋርጧል። በዚህ አውደ ውጊያ የአማራ ፋኖ የቡድን መሣሪያዎች በወታደራዊ ጠበብቶቹ የውባንተ ነፍሥያ የትግል ደሞች ከጠላት የቡድን መሣሪያዎች በእጅጉ ተሽለው የተገኙበት ነው። በተቃራኒው ደግሞ የጠላት ጦር ፋኖን መቋቋም ሢያቅተው የንጹሐን ገበሬዎችን ቤት፣ እንሠሣና ሠብል በቡድን መሣሪያ አውድሟል። ንፁሐንን ገድሏል።

ደጎማ

የብርሐኑ ጁላ ጦር ወታደራዊ መቀመጫውን ደጎማ ላይ አድርጎ ወደ አርባያ፣ጉኋላ፣ ማክሰኝት፣ ሚካኤል ደብር፣ ኪንፋዝ በገላና አምባ ጊዎርጊሥ እየተወረወረ ወገንን ለማጥቃት ይሞክራል።
👉በጥቅምት 29/2017ዓ.ም ጠላት ሌሊት ላይ ከደጎማ ተነሥቶ ወደ አርባያ በለሣ መንቀሳቀሱን የሰሙት የአማራ ፋኖዎቹ የሀብቴ ወልዴና የባዬ ቀናው ልጆች ወረሃላ ላይ ደፈጣ አድርገውበታል። የመጣው የጠላት ጦር አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቷል። የመጣው ኃይል ከተመታ በኋላ ተጨማሪ ኃይል ከደጎማ ሢመጣ የደፈጣው ውጊያ ከደፈጣ ወደ መደበኛ ውጊያ ተቀይሯል። በዚህ አውደ ውጊያ የተለያዩ ዕዞች አንድነትን ፈጥረዋል። መዳኛውም አማራዊ አንድነት ብቻ እንደሆነ አውቀዋል። በዚህ ውጊያ የተሳተፉ፦
1.በሻለቃ አንተነህ ብርሐን የሚመራው የአማራ ፋኖ በጎንደር ጥቁር አምበሳ ብርጌድ
2.የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አካላት በአርበኛ ሚናሥ አለማየሁ የሚመራው ዳግማዊ ቴዎድሮሥ ብርጌድና በሻምበል ሙሉሰው የሚመራው ነብዩ አሣምነው ብርጌድ የሆኑት ጎንደር ዕዞች ናቸው።
👉በጥቅምት 30/2017ዓ.ም በሻለቃ አንተነህ ብርሃን የሚመራው ጥቁር አምበሳ ብርጌድ ከደጎማ ወደ አርባያ እንዲሁም ከአርበያ ደጎማና ወደተለያዩ የአርባያ በለሣ የገጠር ወረዳዎች ለመንቀሳቀሥ የወጣውን የጠላት ጦር የባዬ ቀናው ልጆች በተጠና አውደ ውጊያ ያሰበውን እንዳይፈጽም አድርገውታል።

አለፋ

የብርሐኑ ጁላ ጦር ከአለፋዋ ዋና ከተማ ሻውራ ከተማ ከሌሊቱ 7:00 ተነሥቶ ወደፋኖዎች መጃረሻ ተንቀሳቅሷል። የአማራ ፋኖ በየትኛውም ጋዜና ሁኔታ ሠረጃው ሁሉ ከጠላት በላይ ሆኗል። ወገን ልብ በል ጠላት እየተንቀሳቀሰ ያለው የሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ዕንቁ ሥጦታ የሆነው አርበኛ ሣሙኤል ባለዕድል ወዳለበት ነው። አድዋ ክፍለ ጦር ዋና ወታደራዊ አዛዡ አርበኛ ሣሙኤል ባለዕድል ነው። ሣሚ የአማራ ፋኖ በጎንደር ዋና ወታደራዊ አዛዥና ምክትል ሰብሳቢም ነው። ሣሚ በየትኛውም መንገድ ዕይታው ንሥራዊና አማራዊ ነው። አማራነት ማንን ይመሥላል ከተባለ ተጠየቁ ሣሙኤል ባለዕድልን ነው መልሱ። እንግዲህ ጠላት የተንቀሳቀሰው የአድዋ ክፍለ ጦር አንዲት ሻለቃ ወዳለችበት መዳረሻ ነው። ጠላት የተንቀሳቀሰው አፀደ ማርያም ያለችውን የንጋት ጮራ ብርጌድ አካል የሆነችውን አንዲት ሻለቃ ለማፈን ነበር። ነገር ግን የአማራ ፋኖ መረጃው ደርሶታል። ጠላት አገር አማን ብሎ ሢከንፍ ሌሊት 10:00 ላይ በደፈጣ ርምጃ ተወሰደበት። ውጊያው ጠዋት ላይ ከደፈጣ ወደ መደበኛ ውጊያ ተቀይሯል። የደነገጠው የጁላ ጦር አጋዥ ኃይል ከሻውራ ወደ አፀደ ላከ። አሁንም ንስሮቹ ጠላትን ሢያደባዩ ሌሎች 2 ሻለቃዎች ወደ ወረዳዋ መቀመጫ ሻውራ ገብተዋል። ከባባድ የሚባሉትን ምሽጓች ሰባብረዋል። ከተሰበሩት ከባባድ ምሽጎች መካከል ማንዴላ ሠፈር፣ ማርያም፣ ኬላና አቦዬ ይገኙበታል። ከአፀደ ማርያሙ ውጊያ ተገርፎ ወደ ሻውራ የተመለሰው የጠላት ጦር ሻውራ ላይም ሢመለሥ ከፍተኛ ርምጃ ተወሥዶበታል። የአማራ ፋኖ ከዕለት ዕለት ሥነልቦናው የጠነከረ፣ ትጥቁ የተሟላ፣ ወታደራዊ ጥበብን እየተማረ፤dj የፖለቲካ ሴረኞችን እየለዬ፣ አንድ አማራነትን እየተገበረ ጎጠኞችን ለሕዝብ እየገለጠ ሕዝባዊነቱን በተጨባጭ ለወገንም ለጠላትም እያሳዬ ነው።

፩ አምሐራ
ድላችን በተባበረ አማራዊ ክንዳችን

የአማራ ፋኖ በጎንደር ም/ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኢንጅነር ሀቅአለው ፀጋ አለባቸው

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 18:07


https://youtube.com/live/3eNAusv3LRU?feature=share

Ethio 251 Media

09 Nov, 17:26


ዛሬ በፍራንክፈርት ከተማ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ የምናደረግበት ምክንያት፦

በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ አመራርና ውሳኔ ሰጭነት በአማራ ህዝብ ላይ የሚደረሰውን የጦር ወንጀል ለመቃወምና ለሚመለከተው አካል ሁሉ በግልጽ በአደባይ ድምጻችን ለማሰማት ነው።

በአማራው ቤተሰባችንና ወገናችን ላይ የሚደርሰው የጦር ወንጀል(ጭፍጨፋ) በአስቸኳይ እንዲቆም ነው።
አቢይ አህመድ በ2019 የሠላም Nobel ሽለማት ተሸላሚ መሆኑ ይታዎቃል፣ሆኖም ግን በሠላም ፋንታ በተቀራኒው ፍጹም ዲክታተርና ጦረኛ ፥አረመኔ በመሆን ቀጥሏል።

በኢትዮጵያ የአማራ ክልል ተብሎ በሚጠራው የአማራውን ቤተሰባችንና ወገናችን ፦
በድሮን፥ በተዋጊ ጀት ፥በሚሳኤልና በከባድ መሳሪያ አረጋዊያንን፥ህጻናትን፥ ሴቶችን በግድ በመድፈር በአጠቃላይ አቅመ ደካሞችንና ንጹሀን ቀን በቀን እየጨፈጨፈ ነው።

በጣም የሚያሳዝነውና ልብን የሚሰብረው ጉዳይ ደግሞ የሰብዓዊ መብት ተቆርቆሪነን የሚለው የምዕራቡ መንግስት ማለትም አሜሪካ ፥አውሮፓ(የአውሮፓ ዩኒየን) ሰባዊ መብት ተከራካሪ የዲሞክራሲ (ለሠዎች መብት እኩልነት እንታገላለን ባዮች) (USA,EU,HRW,UNHCR) እንዲሁም ታላላቅ ሚዲያዎች አማራ በማንነቱ ብቻ ተልይቶ ግፍ የሚደርሰበትንና የሚጨፈጨፈውን አማራ ጸጥ ብሎ መመልከቱ ነው።

አብይ አህመድ ፦ከEU,ከ Germany,ከNorewgen በብዙ ሚሊዮን ኦይሮ የሚቆጠር ገንዘብ በEU መሪዋ በ06 October 2023 Urusula von der Lyer (ኡሩዙላ ፎንደርላየረ) press conference ተካሂዶ እርዳታ ለልማትና መልሶ ለማቋቋም በሚል እንዲሁም ከአለም ባንክ አታልሎና ዋሽቶ ከ10'5 ቢሊዮን ዶላር በላይ መውሰዱ ይታወሳል።

እንዲሁም UAE,IRAN ብዙ ሚሊዮን ዶላር ሰጥተውታል፣ግፈኛውና አምባ ገነኑ አብይ አህመድ ግን ለአማራ ህዝብ መጨፍጨፊያ ድሮንና ከባድ መሳሪያ መግዣ በማዋል በአማራ ክልል ህዝብን እየጨፈጨፈ ይገኛል።

ድሮኑና ከባድ መሳሪያውም የሚመጣው ከUAE,ከTurki and ከ IRAN መሆኑን አረጋግጠናል።

በተለይ የUAE መንግስት እሰከአሁንም ድረስ በአረመኔው አብይ አህመድ የበላይነት ለሚመራ መንግስት ከፍተኛ የግብር ከፋይ የሆነውን የአማራ ህዝብ መጨፍጨፊያና ንብረት ማውደሚያ የድሮንና የከባድ መሳሪያ በገፍ እንደሚያቀርብ አረጋግጠናል፣በመሆኑም አብይ አህመድ በአማራ ክልል በአማራው ህዝብ ላይ ጭፍጨፋና ንብረት ማውደም የሚካሂደው በውጭ ሀገር የገንዘብና የጦር መሳሪያ እርዳታ መሆኑን አረጋግጠናል።

በአዲስ ከበባ በሚኖረው የአማራው ቤተሰባችን እና ወገናችን ላይ በአማራ ማንነቱ ብቻ በአረመኔው አብይ አህመድ አገዛዝ ከፍተኛ በደልና ግፍ እየተፈጸመበት ይገኛል።

የአብይ አህመድ የአማራን ህዝብ የሚጨፈጭፈው እንደ UAE እና በሌሎች የውጭ መንግስትታት አገዛ እንጅ በራሱ በምንም አይነት አቅም የለውም፣በመሆኑም የውጭ መንግስታት ለጨፍጫፊ መንግስት የገንዘብም ይሁን የመሳሪያ ርዳታ እንዳተደርጉ በሚጨፈጨፈው የአማራ ህዝብ ስም እንጠይቃለን።


አዘጋጅ በትብብር፦
የአማራ ማህበር በጀርመን
የአማራ ማህበር በሙኒክ
የአማራ ማህበር በበርሊን
የአማራ ማህበር በኑረምበርግ
ተስፋ የአማራ ማህበር በምዕራብ ጀርመን
የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በፍራንክፈርት

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 16:05


https://rumble.com/v5njh0q--9-november-2024-ethio-251-media-251-zare-.html

Ethio 251 Media

09 Nov, 16:05


https://youtube.com/live/cASR3HP57Y0?feature=share

Ethio 251 Media

09 Nov, 11:39


የአማራ ፋኖ በጎጃም በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች እያደረጋቸው ያሉ ትንቅንቆች ባሻገር በርካታ የግንባር ድሎች ተመዝግበዋል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ የአገዛዙ ሠራዊት እንቅስቃሴና የፋኖ ድሎችን በተመለከተ  ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 10:54


የአማራ ፋኖ በጎጃም 1ኛ ክፍለ ጦር የባህር ዳር ብርጌድ የሕዝብ ግንኙነት ፋኖ ሀብታሙ የሱፍ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 10:42


በወሎ ቀጠና ተጋድሎዎቸ ቀጥለዋል።

የካላኮርማ ክፍለ ጦር አናብስቶች ራያ ቆቦ ሮቢት ከተማ በመግባት በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ አድርሰውበታል።

የአማራ ፋኖ በወሎ የካላኮርማ ክፍለጦር የሕዝብ ግንኙነት ሐላፊ ፋኖ አታሎ ፈንታው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆዬታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 08:49


የአማራ ፋኖ በጎንደር አደረጃጀቱን እያሰፋ አዳዲስ ክፍለ ጦሮችን መመስረቱ ተገለፀ።

ራስ ደጀን ክፍለ ጦር በሚንቀሳቀስበት ቀጠና በአዲስ መልክ የተደራጀው አያሌው ብሩ ክፍለጦር መመስረቱን ከጎንደር ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 08:34


የአማራ ፋኖ በጎንደር የጣና ገላውዲዎስ ክፍለጦር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሙሉቀን አለኸኝ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 08:16


በጎንደር ቀጠና ከፍተኛ ተጋድሎ ተደርጓል።

ከአንበሳሜና ወረታ የተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ዋንዛዬ በተባለ መዳረሻ ላይ በቅንጅት መብረቃዊ ጥቃት ተፈፅሞበታል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሀቅአለው ፀጋ አለባቸው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ...

Ethio 251 Media

09 Nov, 07:57


በማዕከላዊ ኢትዮጵያ በጉራጌ ዞን አበሽጌ ወረዳ ዳርጌ ከተማ አማራዎች ላይ ያነጣጠጠረ ጥቃት እየተፈፀመ እንደሆነ ተገለፀ።

ከክልሉ ውጪ ያሉ አማራዎች ላይ የሚደረገውን ጭፍጨፋ የሚመሩት የአገዛዙ ባለስልጣናት እንደሆኑም ተገልጿል።

በአካባቢው የሚገኙ አማራዎች እንግልት ጭፍጨፋና ግድያ፤ ገጀራ በታጠቁ ኃይሎች እየተፈፀመባቸው እንደሚገኝ ከአካባቢው በቃለ- ምልልስ ለኢትዮ 251 ሚዲያ መረጃ አድርሰውናል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

09 Nov, 07:32


ቋሪት የዛሬ የስርዓቱ የድሮን ጥቃት ሰለባ !

በብር አዳማ ከተማ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ አገዛዙ በፈፀመው የድሮን ጥቃት በርካታ ንፁሀን ሲጎዱ ትምህርት ቤቱም ከፍተኛ ውድመት ደርሶበታል።

የአብይ አህመድ ስርዓት ዛሬ ጥቅምት 30
ቀን 2017 ዓ.ም ረፋድ ላይ በቋሪት ወረዳ ብር አዳማ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን ኢላማ አድርጎ በፈፀመው በዚህ ጥቃት በዙሪያው የነበሩ 7 ንፁሃንንም መግደሉን የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊው ፋኖ ዮሀንስ ዓለማየሁ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

08 Nov, 17:02


https://youtube.com/live/zTSXqdk4PQQ?feature=share

Ethio 251 Media

08 Nov, 16:07


የጎንደር ግንባር ተጋድሎዎች ልዩ መረጃ!

ዓለም በርና አካባቢው

በፀዳሉ ደሤ የሚመራው የጎንደር ዕዙ  ጀነራል ነጋ ተገኝ ክፍለ ጦር እና በአማራ ፋኖ በጎንደር (በተመሥገን ውባንተ የሚመራው ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለ ጦርና በሻምበል አምሣሉ የሚመራው ጉና ክፍለ ጦር ዓለም በር ላይ በአንድ የአማራነት ሥሜትና መተማመን የአራዊት ሠራዊቱን ወታደር ለሠዓታት የፈጀን ውጊያ ፈጽመውበታል።

የወገንን ክንድ መቋቋም ያቃተው የአገዛዙ ወታደር ወደ ደብረ ታቦርና ወረታ እግሬ አውጭኝ ብሏል። በዚህ ግምባር የገባው የጠላት ጦር አብረውት ሢንከራተቱ የነበሩ ጓዶቹን አሥከሬን ይዞ መውጣት አልቻለም። የጠላት ጦር የመዋጋት ሥነ ልቦናውን ተሰልቧል። ጠላት በአካልም በቁሥም ኪሣራ ላይ ወድቋል።

እሥቴ ዙሪያ

በዚ ዕለት ከእሥቴ ወጥቶ ወደ ምክሬ፣ ፀዶዬና የተለያዩ ከተማዎችን መግባት ያለመው የጠላት ጦር በጉና ክፍለ ጦር ምክትል ወታደራዊ አዛዣ አርበኛ ቢራራ ደምሤ እየተመራ ሾለክትና ደንጎልት ላይ ውጊያ ሢያደርግ ውሏል። በዚህ አውደ ውጊማ ድል የግላቸው የሆኑት እሥቴ ዴንሳ ብርጌዶች ከእልህ አሥጨራሽ ውጊያ በኋላ ጠላትን ከደንጎልትና ሾለክት ወደ መካነ ኢዬሡሥ ከተማ ከትተውታል።

የምዕራብ ጎንደሯ መተማ በቁርጠኛ ልጆቿ አጣናው ዋሤ ክፍለ ጦር በባሻ ጥጋቡ መንፈሥ ተበረታትተው የአቢይ ሸኔን ወምበር ጠባቂ አራዊት ሠራዊት ሢያሣድዱት ውለዋል።

የአቢይ አሕመድ አራዊት ሠራዊት በቀጠናው ላይ በብዛት ከገባ ሣምንታት ተቆጥረዋል። ጠላት የመጨረሻ አማራጬ ያለውን የምድርና የአዬር ጥቃቶችን እየፈጸመ ይገኛል። ነገር ግን ትግሉን በፍትሕ መሠረት ላይ ያጸናው የአማራ ፋኖ ብርታትና ጥንካሬን እንጅ ድክመትን አላሥተናገደም። ድል ያለ መሥዋዕትነት አይገኝምና የአማራ ፋኖ ከወገን ጠላት ራሱን እየጠበቀና የለዬለት ፋሽሥት አገዛዙን እያብረከረከ ይገኛል። ጠላት ያሰበውና የደረሰበት ውጤት የውቅያኖሥና የኩሬ ልዩነት አለው። ጠላት አሉኝ ያላቸውን ዘመናዊ ሠላዮችና መረጃዎች በገፍ አሰማርቷል። ነገር ግን ይህ ሁሉ የጠላት አካሄድ ከአማራ ፋኖ ዓይን የተሰወረ አልሆነም።

ድላችን በተባበረ አማራዊ ክንዳችን

የአማራ ፋኖ በጎንደር ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ፋኖ ሃቅአለው ፀጋ አለባቸው ለጣቢያችን የላከው መረጃ!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

08 Nov, 15:16


ፀበልተኞቹ በልተው ጠጥተው እየጨፈሩ ¡¡¡

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

08 Nov, 14:27


የጀነራሎቹ የዕርስ በዕርስ ተኩስ በወልድያ !

የአብይ የግል ጀነራሎች የግል ተኩስ ከፍተዋል።

ትላንትና ቃሊም ላይ በተደረገ ውጊያ በርካታ ሰራዊቱ ሙትና ምርኮኛ የሆነበት የሰሜን ምስራቅ ዕዝ ጀነራሎች እርስ በእርስ እንደገጠሙ የአይን እማኞች ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልፀዋል።

ወልድያ እንጨት ተራ አርሶ አደር ህንፃ ሆቴል በብስጭት ሲጠጡ ያደሩት ጀነራሎቹ ትናንት በደረሰባቸው ከፍተኛ ምርኮና የግንባር ሽንፈት ሲጨቃጨቁ ካደሩፐ በኋላ ጠዋት ሁለት ሰዓት ገደማ "ሀይል ጨምርልኝ ስልህ አልጨመርክልኝም"  "ብጨምርልህም አስማርከህ ነው የምትመጣው፤ መድፍ ሳስተኩስልህ አልነበር ወይ" በሚል እርስ በእርስ ከቃል ወደ መሳርያ ተሸጋግረው እንደገጠሙ ምንጮች ለኢትዮ 251 ሚዲያ አረጋግጠዋል።

የጀነራሎቹ ግብግብ ወደ አጃቢዎቻቸውም ወርዶ እስካሁን አምስት አጃቢዎቻቸውን እርስ በእርስ አስተኳኩሰው እንዳገዳደሉ የአይን እማኞቹ ገልፀዋል።

የዓይን እማኞች የነበረውን ሒደት ሲገልፁም ግማሾቹ እዚያው ያደሩ ሲሆን  የተወሰኑት ጄነራሎች ደግሞ ንጋት አካባቢ ወደ ሆቴሉ እንደመጡና ሆቴል ላይ ከሴት ጋር ሲያገኟቸው " እናንተ ሴት ጭን ስር ሆናችሁ ሰራዊቱ ያልቃል" በሚል ነው ጭቅጭቁ የተነሳውና ወደ መገዳደል ያመራው ሲሉ በቦታው ላይ የነበሩ የዓይን እማኞች ለ251 ገልፀዋል።

እርስ በእርስ መገዳደሉና የቡድን ተኩሱ ለፍተኛ ውጥረቱ ወደታችኛው ሰራዊት እየወረደ በመምጣቱ ሀራ የሚኘው የሰሜን ምስራቅ እዝ አዛዥ ጀነራል አሰፋ ቸኮል ነገሩን ለማርገብ እየከነፈ ወደ ወልድያ እያቀና እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

08 Nov, 13:48


የአማራ ፋኖ አዳዲስ ልዩ ኮማንዶዎችን ማስመረቁን ቀጥሏል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የሀዲስ አለማየሁ የአብራጂት ብርጌድ አባላት ለተከታታይ 5 ወራት ሲያሰለጥኗቸው የቆዩትን የመብረቅ ኮማንዶዎችን በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።

በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ የሀዲስ አለማየሁ ክፍለጦር አመራሮች ተገኝተው ንግግር አድርዋል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 18:04


ሰበር ዜና ወልድያ !

ወልድያ ላይ ሰርጂካል ኦፕሬሽን እየተፈፀመ ነው!

የአማራ ፋኖ በወሎ ክፍለጦሮች ማምሻቸውን ወልደያ ከተማ ዘልቀው በመግባት በተመረጡ ቦታዎች ልዩ ሰርጂካል ኦፕሬሽን እየሰሩ መሆናቸውን የአማራ ፋኖ በወሎ አሳምነው ክፍለጦር ሕ/ግ ኃላፊ ፋኖ ንጉሥ አበራ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

በቃሊም ግንባር አስደናቂ ጀብዱ ሲከውን የዋለው የአማራ ፋኖ በወሎ ማምሻውን ወልድያ ከተማ ላይ አስገራሚ ጀብዱ እየፈፀመ እንደሚገኝ ፋኖ ንጉሥ አበራ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

የአማራ ፋኖ በወሎ በጥቅምት ወር ብቻ ሶስት ጊዜ የሰሜን ወሎ ዞን መቀመጫ በሆነችው ወልድያ በመግባት ልዩ ኦፕሬሽን መፈፀሙ የሚታወስ ነው፡፡

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 16:53


በርካታ የግንባር ልዩ መረጃዎችን ይዘናል፣ ገባ ገባ በሉ!

https://www.youtube.com/live/rBdKiJl4jak?feature=shared

Ethio 251 Media

07 Nov, 16:15


“ደሞ ምንድነው የባንዳ ቁጣ
ዘንጥለውና የመጣው ይምጣ”

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 15:38


በድጋሚ በምርኮ የተጥለቀለቀው የቃሊም ግንባር

በዛሬው ዕለት ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በቃሊምና ዙሪያ አስደናቂ ተጋድሎ በማድረግ አስደናቂ ጀብዱ መሰራቱን የአማራ ፋኖ በወሎ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ በለጠ ሸጋው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

በዋርካው ምሬ ወዳጆ የሚመራው የአማራ ፋኖ በወሎ ዞብል አምባ ክፍለጦር፣ አሳምነው ክፍለጦር እና ታጠቅ ክፍለጦር የተውጣጡ የሻንበል ኃይሎች በውጊያ የተሳተፉ ሲሆን ውጊያውን የአማራ ፋኖ በወሎ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ በለጠ ሸጋው፣ ኮሎኔል ሞገስ ዘገዬ፣ ኮሎኔል ፈንታው መኩዬ በአስገራሚ መናበብ እንደመሩት የአማራ ፋኖ በወሎ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው ለጣቢያችን ገልጿል።

በዚህ ውጊያም ከፋኖ አንድ አባል ሲሰዋ የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ ሰራዊት በብዛት ረግፎል፡፡ ውጊያ አሁንም እንደቀጠለ ቢሆንም ብሬንና ስናይፐሮች ተማርከዋል፣ 36 ምርኮኛ፣ 1ሺ 5 መቶ በላይ የዲሽቃ ተተኳሽ፣ 47 በላይ ክላሽንኮቭ መሳሪያ፣ የብሬን ተተኳሽ ከ6ሺ በላይ፣ የክላሽ 5ሺ በላይ፣ F1 ቦንብ 50፣ ወታደራዊ ሻንጣ 190 እስካሁን ተገኝቶል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ፋኖ በለጠ ሸጋው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

በዚህ ውጊያ የሰሜን ምስራቅ እዝ ሁለተኛ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጣዕመ በጀግኖቹ ተጋድሎ ሲደመሰስ፤ አጃቢዎቹንና የሬዲዮ ኦፕሬተሮች ተማርከዋል ሲል ፋኖ በለጠ ሸጋው የገለጸ ሲሆን "ውጊያው ገና አልተጠናቀቀም በየጢሻው የወደቀውን ትጥቅ እየሰበሰብን ነው፤ አሁን ከአገኘናቸው በላይ ተጨማሪ ድሎችን እንደምናስገንዘብ ተስፋ አለን ብሏል።
በዚሁ የቃሊም ግንባር ጷጉሜ 2 ቀን 2016 ዓ.ም የ48ኛ ክፍለጦር ም/አዛዥ ኮሎኔል ሰለሞንና ከ100 በላይ ሰራዊት የተደመሰሰበት፣ ከ150 በላይ ሰራዊት የተማረከበት፣ 200 ጥቁር ክላሽ፣ 5 ስናይፐር፣ 4 ብሬን፣ አንድ ዲሽቃ፣ ሁለት ሞርተር የተገኘበት ድል እንደሆነ ፋኖ በለጠ ሸጋው ገልጿል።

ፋኖ አበበ ፈንታው በበኩሉ አገዛዙ ከፍተኛ ኪሳራ ሲደርስበት በዘፈቀደ ከባድ መሳሪያዎችን እያስወነጨፈ ንጹሃን ላይ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሰ መሆኑን ለጣቢያችን ገልጿል፤ በተጨማሪም አጠቃላይ በወሎ ቀጠና በንጹሃን ሕዝባችን ላይና በአገልግሎት ሰጭ ተቋማት የሚፈፀሙ የድሮን ጭፍጨፋዎች ከአፋር ሰመራ እንደመሆናቸው የአፋር ሕዝብ ከአፋር በመነሳት የሚፈፀመው የድሮን ጥቃት እንዲያስቆም ወንድም ሕዝባችን እንጠይቃለን ሲል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 14:38


የዛሬ መግቢያ ነው።

https://youtube.com/@ethio251media69?si=bB9Ne4AnFcRK1nd9

Ethio 251 Media

07 Nov, 14:17


ሰበር ዜና!

ሰሜን ምስራቅ እዝ ሁለተኛ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጣዕመ በጀግኖቹ ተጋድሎ ተደመሰሰ!

የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ የቃሊሙ ታላቅ ድል በዛሬው እለትም ተደግሟል::

የበላጎው ባለታሪኮች ዞብል አምባ ክፍለጦርና አሳምነው ክፍለጦር ታጠቅ ክፍለጦርን ተጠባባቂ አድርገው በጋራ በፈፀሙት ታላቅ ተጋድሎ ከወልድያ ከተማ በቅርብ ርቀት የምትገኘው የራያ ቆቦዋ ቃሊም ከተማን ለመቆጣጠር የመጣው ጠላት በጀግኖቹ በርካታ ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ሆኗል::

ከበላጎ ተራራ ስር የምትገኘዉን ቃሊም ከተማ ለመቆጣጠር አስቦ የመጣው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ አዲስ ምልምል ሰራዊት በጀግኖቹ የዋርካው ምሬ ወዳጆ ልጆች አይቀጡ ቅጣት ተቀጥቶ 48ኛ ክፍለጦር 5ኛ እና 2ኛ ሻለቆች ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ተደምስሰዋል:: በአዲሱ አመት 2017 አ.ም መባቻ ቃሊም ከተማና አካባቢው ላይ 48ኛ ክፍለጦር 4ኛ ሻለቃ በብ/ጀ አሳምነው ፅጌ ክፍለጦር፣ የጊራናው ባለሽርጡ ክፍለጦርና ታጠቅ ክፍለጦር ሙሉ ለሙሉ መማረኳና መደምሰሷ የሚታወቅ ነው::

በጀኔራል አሰፋ ቸኮል የሚመራው ሰሜን ምስራቅ እዝ ሁለተኛ ኮር ምክትል አዛዥ ኮሎኔል ጣእመ በጀግኖቹ ተጋድሎ የተደመሰሰ ሲሆን ሁሉም አጃቢዎቹ እጅ ሰጥተው ይገኛሉ::

በተጋድሎው በርካታ የጠላት ሃይል ሙትና ቁስለኛ የሆነ ሲሆን ከምርኮ የተረፈዉም ፈርጥጦ ወልድያ ከተማ ገብቷል:: በርካታ ቁጥር ያለው ምርኮኛ በእጃችን ያለ ሲሆን በቀጣይ ይፋ የምናደርግም ይሆናል ሲሉ የዞብል አምባ ክፍለጦርና የአሳምነው ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነቶች ፋኖ ሃብተማርያም መንበሩ እና ፋኖ ንጉስ አበራ ገልፀዋል::

በምርኮ የተገኙ ድሎች

-ስናይፐርና ብሬን
-ለጊዜው ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ ነፍስ ወከፍ ክላሽ
-ለጊዜው ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ የብሬንና የክላሽ ተተኳሽና የዲሽቃ ተተኳሽ

የህልዉና ተጋድሎው እስከ ነፃነት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 13:09


ሰበር ዜና

የአምቦ ሜዳ ከተማ በፋኖ ቁጥጥር ስር ገብታለች።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ እቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር በትላንትናው ዕለት ጥቅምት 27 ቀን 2017 ዓ.ም እና በዛሬው ዕለት ጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ ዘመንና እብናት ዙሪያ በተደረገ ትንቅንቅ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለጦር አንበሳው ሊቦከምከም ብርጌድ አገዛዙ ሰፍሮበት የነበረውን አምቦ ሜዳ ከተማን በማስለቀቅ ወደ አዲስ ዘመን ከተማ እንዲፈረጠጥ ማድረጉን የክፍለጦሩ ቃል አቀባይ ፋኖ መልካሙ ጣሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል።

ከአምቦ ሜዳ ከተማ አገዛዙን በማስለቀቅ አዲስ ዘመን ያስፈረጠጠው ኃይል መንገድ መሪ የነበረውን የአዲስ ዘመን ከተማ ሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊ ቤትን በልዩ ኦፕሬሽን ሚኒሻዎችን ጨምሮ መኖሪያ ቤቱን ሙሉ ለሙሉ ማውደማቸውን ፋኖ መልካሙ ጣሴ ለጣቢያችን ገልጿል።

ፋኖ መልካሙ ጣሴ በአንክሮት ከገለጻቸው ጉዳዮች መካከል "በአየር ኃይልና በእግረኛ ኃይል ያልተበገረውንና ጀብደኛውን የሊቦከምከም ብርጌድን አንዳንድ (በስም ጠቅሶ) ሚዲያዎች ተቋማችን በሴራ የማፍረስ ስራ እየሰሩብን ነው፤ እነዚህ ሚዲያዎች በተደጋጋሚም ከዚህ ድርጊታችሁ ታቀቡ ብንላቸውም፤ አሁንም ግን የማፍረስ ስራቸውን ቀጥለውበታል፤ ሕዝባችን ያስቁምልን" ብሏል።

ዝርዝር መረጃዎች አሉት በ251 ዛሬ ይጠብቁን!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 12:19


አስደናቂ ሰበር ዜና አለ ይጠብቁን!

Ethio 251 Media

07 Nov, 11:34


የብልፅግና ስርዓት ፍርሰት ማሳያ ከፍተኛ አመራሮቹ የአገዛዙን መዋቅር እየበተኑ ህዝባዊ ትግሉን እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።

የአማራ ክልል የጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የአማራ ሃኪሞች ማህበር መስራች ዶ/ር ጋሹ ክንዴም የአማራ ፋኖ በጎጃምን ተቀላቅሏል።

ዝርዝር መረጃው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ደርሷል።

ተከታተሉት......

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 11:08


የአገዛዙን ሠራዊት እየከዱ የፋኖ ኃይሎችን የሚቀላቀሉ የብልፅግና ሠራዊት አባላት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የከሰም ክፍለ ጦር የነበልባል ብርጌድን የተቀላቀሉ የአገዛዙ ሠራዊት ምስክርነታቸውን ለፋኖ አመራሮች ሰጥተዋል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 10:51


የአማራ ፋኖ በጎጃም በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች እያደረጋቸው ያሉ ትንቅንቆች ባሻገር በርካታ የግንባር ድሎች ተመዝግበዋል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ የአገዛዙ ሠራዊት እንቅስቃሴና የፋኖ ድሎችን በተመለከተ  ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 10:37


የአማራ ፋኖ በጎጃም የ5ተኛ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ደሳለው ሙሉጌታ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 09:51


የአማራ ፋኖ በጎጃም!

የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አመራሮችና በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች ጥቅምት 27/2017ዓም በእናርጅ እናውጋ ወረዳ የሚገኜው ሶማ ብርጌድን የአመታዊ ግዳጅ እና የወደፌት የትግል ጉዞ በማስመልከት ከሶማ ብርጌድ ፋኖ አባላቶች ጋር ውይይት በማድርግ በብርጌዱ ውስጥ የነበሩ ችግሮችን ነቅሰው ጥለዋል።

በዚህ የስብሰባ ውይይት የተገኙት የአማራ ፋኖ በጎጃም ከፍተኛ አመራሮችና የበላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር አመራሮች በሶማ ብርጌድ የፋኖ አባላቱ የተሰጣቸውን  ጥያቄ ተቀብለው የሶማ ብርጌድን አመራር እሪፎረም አድርገዋል።በዚህም የሶማ ብርጌድ የአመራር እሪፎርም የተመርጡ ስም ዝርዝር:-

1,ሰብሳቢ---- እርቂሁን ጫኔ
2,ም/ል ሰብሳቢ---- ወንዴ የሽዋስ
3,ጦር አዛዥ---- መቶ አለቃ ይበልጣል ተፈራ
4,ም/ል ጦር አዛዥ----አምሳ አለቃ ደሴ ሞላ
5,ፖለቲካ ዘርፍ ሀላፌ---- መ/ር መንበር ልዕውል
6,ህዝብ ግንኙነት ሀላፌ---- ይታያል አየሁ
7,አደርጃጀት ዘርፍ---- ሰውነት ተሾመ
8,አስተዳደር---- አምሳ አለቃ አለቃ ልውየ
9,ፋይናስ ዘርፍ--- የስጋት ጫኔ
10,ሎጀስቲክ ዘርፍ --- ወንዴ ሀብታም
11,ቀጠናዊ ትስስር---- ባልኬ በላይነህ
12,ፅ/ቤት ሀላፌ---- ሙሉቀን ካሳ
13,የሰው ሀይል ዘርፍ---- ኪሩቤል ፍሬው
14,ኦርድናስ ---- ተዋበ ሞላ
15,ዘመቻ ---- ይከበር ሀይሌ
16,ስልጠና መምሪያ--- አትንኩት ደመቀ
17,መርጃ ደንነት----........... የአማራ ፋኖ በጎጃም በላይ ዘለቀ 8ኛ ክፍለ ጦር አመራር ሆነው ተመርጠዋል።

መረጃው የአማራ ፋኖ በጎጃም የ8ተኛ በላይ ዘለቀ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ፋኖ ይበልጣል ጌቴ ነው።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 09:11


የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቋራ ኦሜድላ ክፍለጦር ለ6 ወራት ሲያሰለጥናቸው የነበሩትን ልዩ ኮማንዶዎችን አስመርቋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ ላይ:-
* የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ዋና አዛዥ አርበኛ ሀብቴ ወልዴ
* የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ም/አዛዥ አርበኛ ተሾመ አበባው
* የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ደረጄ በላይ
* የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የስልጠና መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ፀዳሉ ደሴ እና ሌሎች አመራሮች ተገኝተው በመድረኩ ላይ የትግል አቅጣጫ የሠራዊቱን ሞራል የሚያነቃቃ ንግግር አድርገዋል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

07 Nov, 08:28


የድጋፍ አማራጮች !

ኢትዮ 251 ሚዲያን ለመደገፍ አማራጮችን ስትጠይቁን ለነበራችሁ ቤተሰቦቻችን ሁሉ !

ድጋፋችሁን ቀጥታ በባንክ አካውንት ወይንም ከስር በተቀመጠው ሊንክ በመግባት ኢትዮ 251 ሚዲያ በሚዲያው ዘርፍ የሚያደርገውን ትግል ትደግፉ ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።


Bank Acct Info: Chase Bank
Account number
675535275
Routing number
322271627

Donation with Credit/PayPal
https://www.paypal.com/donate?hosted_button_id=E9D9PAGHFM35N

Ethio 251 Media

06 Nov, 17:12


https://rumble.com/v5mhw5e--6-november-2024-251-zare-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

06 Nov, 16:49


ቤተሰብ መግቢያችንን እስክትሞሉልን በመጠባበቅ ላይ ነን::

በፍጥነት 1000 አስገቡልን::

https://youtube.com/@ethio251media69?si=bB9Ne4AnFcRK1nd9

Ethio 251 Media

06 Nov, 15:30


ሰበር ዜና!

በሰሜን ወሎ ዞን የወልድያ ከተማ የጣይቱ ብጡል ክፍለ ከተማ ሚሊሻ ፅ/ቤት ሃላፊ ከነአጃቢዎቹና ከአንድ ፖሊስ ጋር ባልታወቁ ሃይሎች በቦምብ እርምጃ ተወሰደባቸው::

እርምጃው የተወሰደው ጣይቱ ብጡል ት/ቤት አካባቢ ጥቅምት 26/2017 አ.ም ከቀኑ 11:30 አካባቢ ሲሆን በጥቃቱ ሁሉም ከባድና ቀላል ቁስለኛ ሆነው ወልድያ ሆስፒታል በህክምና ላይ እንደሚገኙ “ያልታወቁ ሃይሎች” ብለው ራሳቸውን የሚጠሩት መረጃውን ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል::

በቀጣይም በአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀመ ካለው የአብይ አህመዱ የአንድ ቡድን አገዛዝ ጋር የተባበረና ዙፋን አስጠባቂ የሆነው ሁሉ ላይ እርምጃው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና የመረጃና የደህንነት መረቡን የመበጣጠስ ስራ እንደሚሰሩ “ያልታወቁ ሃይሎች” ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋለዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

06 Nov, 14:45


የለንደን ፋኖዎች (LONDON FANO) ታሪክ መስራታቸውን ቀጥለዋል።

በ UK የዓለም የቱሪዝምና የቢዝነስ ቀን በሚካሄድበት መድረክ ላይ ለወገናቸው ድምፅ በመሆን የተለመደ የጀግንነት ተግባራቸውን በመፈፀም የአብይ አህመድ አገዛዝን እያጋለጡት ቀጥለዋል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 17:08


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በጎጃም 5ተኛ ክፍለጦር የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ የሆነችውን ፍኖተ ሰላም ከተማን ከደቂቃዎች በፊት ተቆጣጥሯል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 16:30


https://youtube.com/live/mvNbz3B1yio?feature=share

Ethio 251 Media

05 Nov, 15:34


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በጎጃም 5ተኛ ክፍለጦር የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና ከተማ የሆነችውን ፍኖተ ሰላም ከተማን ከደቂቃዎች በፊት ተቆጣጥሯል።

ዝርዝር መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 14:14


በሸዋ ቀጠና የሚደረጉ ተጋድሎና ትንቅንቆች ቀጥለዋል።

ከፍተኛ ወታደራዊ ድል የተገኘባቸው የግንባር ተጋድሎዎች መኖራቸውም ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ዋና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አርበኛ አበበ ሙላት በግንባር ተጋድሎዎችና የድል ውጤቶች ዙሪያ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 13:04


የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ነፃ ባወጣቸው ቀጠናዎች የሲቪል አደረጃጀትና መዋቅር እየተዘረጋ ይገኛል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ነፃ ባወጣቸው ቀበሌዎች ከህዝብ ጋር ውይይት በማድረግ ህዝባዊ አደረጃጀት ማዋቀራቸው ተገልጿል።

በመድረኩ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ ሻለቃ ሙሉቀን ቢራራን ጨምሮ የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተው ንግግር አድርገዋል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 12:45


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለው የህልዉና ተጋድሎ ሙጃ ከተማን ተቆጣጥሮ በርካታ ድሎችን ተጎናፀፈ::

በዋርካው ምሬ ወዳጆ የሚመራው የአማራ ፋኖ በወሎ ዛሬ ጥቅምት 26/ 2017 አ.ም ማለዳ ላይ በተጀመረ መደበኛ ዉጊያ በቀላል መስዋዕትነትና ባጭር ሰአት ከተማዋን ሙሉ ለሙሉ በመቆጣጠር ፖሊስ ጣቢያዉንና የተለያዩ የጠላት መሰረት የሆኑ ቦታዎችን ሰብሮ በመግባት በርካታ ድሎችን ተጎናጽፏል::

የጠላት ቁልፍና መሰረት የሆነዉን ወታደራዊ ቦታ የሰሜን ወሎ ዞን ጊዳን ወረዳን ተቆጣጥሮ የሚገኘው የአማራ ፋኖ በወሎ በዛሬው እለት ደግሞ የከተማ መቀመጫው የሆነችዉን ሙጃ ከተማን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሮ ጠላት ላይ ከባድ ዉጊያ በመክፈት በርካታ ሙትና ቁስለኛ በማድረግ እንዲሁም በመማረክ ሰብአዊና ቁሳቂ ኪሳራ አድርሶበታል::

በኮማንዶ ዘላለም የሚመራው ተከዜ ክ/ጦር በሻለቃ ብርሃን የሚመራው ጥራሪ ክ/ጦር እንዲሁም ከማረጉ ተማረ ክ/ጦር በፋኖ ምስጋን የሚመራ ሻለቃ በአጠቃላይ በላስታ አሳምነው ኮር ስር ያሉ ግዳጁ ላይ አሃዶቻቸዉን ያሳተፉ ክፍለጦሮች ናቸው::

ከዚህ በተጨማሪ በፋኖ ካሳ አበበ የሚመራው ሃውጃኖ ክፍለጦርና በፋኖ ጌታሁን ሲሳይ የሚመራው አሳምነው ክፍለጦርን ጨምሮ ከሁሉም አሃዶች የተውጣጡ ሻለቆች በጋራ የፈፀሙት ግዳጅ ነው::

ከጠላት ኪሳራ አኳያ

1. እስካሁን በቁጥር ያልታወቀ በርካታ ሙትና ቁስለኛ ሆኗል::

2. ሁለት የጠላት መኪና የተቃጠለና አንድ የጠላት ዲሽቃ ከጥራሪ ክፍለጦር መካናይዝድ ቡድን በተወነጨፈ ሞርታር ሙሉ ለሙሉ ወድሟል::

3. ብልፅግና የአማራን ህዝብ ለማጥፋት የሚጠቀማቸዉ የቢሮ ሰነዶች ከምንፈልጋቸው ዉጭ ያሉት ፖሊስ ጣቢያዉን ጨምሮ ሙሉ ለሙሉ ወድሟል::

ምርኮን በተመለከተ
1. ጥራሪ ክ/ጦር 22 ከላሽ አንድ ጂመስሪ በምርኮ አግኝታለች::

2. ተከዜ ክ/ጦር ከአስር በላይ ከላሾችን በምርኮ አግኝታለች::

3. ከ20 በላይ ሆድ አደር ሚሊሻ ተማርኳል::
4. የአሳምነው እና ሃውጃኖ ክፍለጦር አሃዶች ቁጥሩ በዉል ያልታወቀ የነፍስ ወከፍ ክላሽ ማርከዋል::

ሌላው አስገራሚ ነገር የተከበበዉን የጠላት ሃይል ለማዉጣት ከድልብ በኩል የመጣው ዙ23 የራሱን ወገን መትቷል: ይህ የሆነው ደግሞ ፋኖዎች በጥበብ የነበሩበትን ቦታ ለቀው ለጠላት ቦታዉን በመስጠታቸዉ ነው። በዚህም ዙ23ቱ የራሱን ወገን በርካታዉን ጨፍጭፎታል።

• መሐል ሳይንት

የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ክንፍ የሆነው አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ጀብዱ መፈፀሙ ተገልጿል።
የአማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር አካል የሆነው በመቅደላ ወረዳ የሚንቀሳቀሰው በፋኖ በለጠ ምትክ የሚመራው ሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ባንዳዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።

አድማ ብተና ጋር ተጠርንፈዉ የነበሩ የብልፅግና ባንዳዎች ጤፍ ሊያሳጭዱ  አስፈቅደው ወደ ቤተሰብ እንደመጡነው  እርምጃ የወሰድንባቸዉ ሲል የሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ገልጿል።  ደጋግመን ጥሪ አድርገን ስለነበር ጥሪያችንን ሳይቀበሉ በመቅረታቸውና ወደወጡበት ማህበረሰብ ተመልሰው የመምጣት ፍላጎት ስለሌላቸው  የማያደግም እርምጃ ለመውሰድ ተገደናል ሲል ብርጌዱ አክሎም ገልጿል።

በሌላ ምእራብ ወሎ ኮር ተጋድሎ መሃል ሳይንት ወረዳ ደንሳ ከተማ ዛሬ አዳሩን ማለትም ሰኞ ለማክሰኞ አጥቢያ ለአንድ ቡድን አገዛዙና ለሆዳቸው አድረው ህዝባቸውን ሲጨፈጭፉና ሲያስጨፈጭፉ የከረመው ሆድ አምላኩ የሆኑ ሚሊሻዎች አዳሩን አይቀጡ ቅጣት ተቀጥተው አድረዋል። በርካታ የጠላት ሃይልም ሙትና ቁስለኛ ሆነዋል::

የህልዉና ተጋድሎው እስከ ነፃነት ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 12:44


አማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር የአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ ዋና ከተማ ከሆነችው መኮይ ከተማና ዙሪያ ላይ በሚገኘው የአገዛዙ ሀይል ላይ ልዩ ኦፐሬሽን በመስራት ከፍተኛ ድል አስመዝግበዋል።

 በክፍለጦሩ ስር ያሉ ፊትአውራሪ ገበየው ብርጌድና ብሩኬ ደምሴ ብርጌድ በተሳተፉበት አስደማሚ ኦፐሬሽን በባቡር ስቴሽንና በአፍሶ ቀበሌ ጫፍ የሰፈሩ ቀይ ቦኔት ኮማንዶዎች በደረሰባቸው ከፍተኛ ምት ሙትና ቁስለኛቸውን እየጫኑ ወደ ሙያና ቴክኒክ ሲያመላልሱ መዋላቸው ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አስቴጉማ ተራራ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ አብርሃም አሰፋ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 12:30


ሰበር ዜና!

ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ቲሊሊ ከተማ ላይ በተደረገው ዉጊያ አሸባሪዉ ቡድን በግንባር አልችል ብሎ ሙትና ቁስለኛ ሲሆን በዚህ ብስጭት ከባድ መሳሪያ በመወርወር የንፁሃንን መጠለያ ቤት በዚህ ልክ አፍርሶ ሶስት የቤተሰብ አባላትን እማወራና አባወራውን ህፃን ልጅ ጨምሮ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶባቸዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 12:15


የድሮን ጥቃት ሸዋ !

አገዛዙ ዛሬም ጭፍጨፋው ተባብሷል።

ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓም በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቀወት ወረዳ የለን ቀበሌ ረፋዱ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት በርካቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ኢትዮ 251 ሚዲያ ሰምታለች።

ይህ የሀብትና ንብረት ውድመትና የንፁሀን ፍጅት ያስተናገደው የድሮን ጭፍጨፋም 5 ንፁሀን ወዲያው ሲገደሉበት ሌሎችም ተጎድተዋል ተብሏል።

በዝርዝር እንመለሳለን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

Ethio 251 Media

05 Nov, 12:11


ሰበር ዜና!

ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ቲሊሊ ከተማ ላይ በተደረገው ዉጊያ አሸባሪዉ ቡድን በግንባር አልችል ብሎ ሙትና ቁስለኛ ሲሆን በዚህ ብስጭት ከባድ መሳሪያ በመወርወር የንፁሃንን መጠለያ ቤት በዚህ ልክ አፍርሶ ሶስት የቤተሰብ አባላትን እማወራና አባወራውን ህፃን ልጅ ጨምሮ ከፍተኛ ጉዳት አድርሶባቸዋል።

በተንቀሳቃሽ ምስል ማስረጃ እንመለሳለን!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 12:07


የድል ዜና!!

የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ክንፍ የሆነው አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ጀብዱ ፈፀመ!

የአማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ክንፍ የሆነው በመቅደላ ወረዳ የሚንቀሳቀሰው በፋኖ በለጠ ምትክ የሚመራው ሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ባንዳዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን ለኢትዮ 251 ሚዲያ አስታወቀ።

አድማ ብተና ጋር ተጠርንፈዉ የነበሩ የብልፅግና ባንዳዎች ጤፍ ሊያሳጭዱ  አስፈቅደው ወደ ቤተሰብ እንደመጡነው  እርምጃ የወሰደባቸዉ ሲል የሸህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ከፍተኛ አመራር ለጣቢያችን ገልጿል።  ደጋግመን ጥሪ አድርገን ስለነበር ጥሪያችንን ሳይቀበሉ በመቅረታቸውና ወደወጡበት ማህበረሰብ ተመልሰው የመምጣት ፍላጎት ስለሌላቸው  የማያደግም እርምጃ ለመውሰድ ተገደናል ሲል ከፍተኛ አመራሩ አክሎ ገልጿል።

እርምጃ የተወሰደባቸው ባንዳዎች፦
1ኛ መስፍን ወዳጀ
2ኛ ክንዱ ወዳጀ የሚባሉ ሲሆን  ዛሬ በቀን 26 2017 አመተ ምህረት ንጋት 11:00 ሰአት  ላይ መቅደላ ወረዳ 025 ጦርቅ ቀበሌ   የረንዝ በተባለ ልዩ ቦታ ላይ እስከወዳኛው ላይመለሱ የተሸኙ ሲሆን  ከነዚህ በተጨማሪም ሶስት ቁስለኛ እንዳለ ለማወቅ ተችሏል።

ይህ በእንድህ እንዳለ በመሃል ሳይንት ወረዳ ደንሳ ከተማ ዛሬ አዳሩን ማለትም ሰኞ ለማክሰኞ አጥቢያ ለአገዛዙ ተገርደው ህዝባቸውን ሲጨፈጭፉና ሲያስጨፈጭፉ የከረሙት  ሆድ አምላኩ የሆነት  ሚሊሻዎች እርስበርሳቸው አዳራቸውን ሲታኮሱ ማደራቸው ታውቋል። በዚህም የደረሰው ጉዳት በውል ባይታወቅም ነገር ግን ከ039 አህዮ ቀበሌ የዘለቀ አስናቀ የተባለ  አንድ ሚሊሻ መሞቱን ምንጮች ለ ኢትዮ 251 ሚዲያ አድርሰዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 11:58


በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ (UAE) ወታደራዊ ስልጠና የተሰጣቸው የአብይ አህመድ ኮማንዶዎች በአማራ ፋኖ የደህንነት ክንፍ በቁጥጥር ስር እየዋሉ ይገኛሉ።

በንፁሀን ላይ ጭፍጨፋ ሲፈፅምና ሲያስተባብር የነበረው 105ኛ ክፍለ ጦር ልዩ ዘመቻ መሪ በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የደህንነት መዋቅር ከበርካታ ሰነዶች ጋር በቁጥጥር ስር መዋሉ ተረጋግጧል።

ከአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አባቡ አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 11:36


በንፁሃን ደም የሰከረው የአብይ አህመድ ቡድን እብደቱን ቀጥሎበታል።

ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም በደቡብ አቸፈር ወረዳ በዝብስት ንዑስ ከተማ 43 ሲቪሊያንን በጅምላ ጨፍጭፏል። 21 ያህክሉ ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በከተማዋ የተለያዩ አካባቢወች በተከታታይነት በተደረገ የድሮን ጥቃት ጤናጣቢያ እና ትምህርት ቤትን ጨምሮ በርካታ የግለሰብ ቤቶችም ወድመዋል።

ከዚህ በፊት በዚሁ ደቡብ አቸፈር ወረዳ ዲላሞ (ላሊበላ) ላይ አምስት ንፁሃንን መጨፍጨፉ ይታወቃል::

የአማራ ህዝብ ይሔን ኢትኖ ፋሽስት ቡድን አምርሮ መታገል እና ማስወገድ ታሪካዊ ግዴታው ነው።

ፋኖ አስረስ አማረ
የአማራ ፋኖ በጎጃም ም/ሰብሳቢና የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 11:29


የአማራ ፋኖ የካራማራ ክፍለ ጦር ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ  ደቦል ጉንዶ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 11:20


በጎንደር ቀጠና ከጠላት ሃይል ዲሽቃ ተማርኳል።

የትግሉ ደረጃ እያደገ በክላሽ የጀመረው የአማራ ፋኖ ተጋድሎ ከጠላት እየማረከ ከባድ መሳሪያዎችን እየታጠቀ ይገኛል።

ከካራማራ ክፍለ ጦር ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር አቅርቦታል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 10:58


“እየተዋጋን እንሰለጥናለን፣ እየሰለጠን እንዋጋለን” ፋኖ

የአማራ ፋኖ በወሎ አዲስ ምልምል የፋኖ የሰራዊት አባላት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

05 Nov, 10:14


ቆንጆዎቹ እየመጡ ነው!

የአማራ ፋኖ የጀመረዉን ትግል ዳር ለማድረስ ሰራዊታችን ማዘመን እንዳለብን ይታወቃል፣ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቋራ ኦሜዲላ ክፍለ ጦር 1ኛ ዙር ልዩ ኮማንዶዎች እና በዳግማዊ ቴድዎድሮስ ብርጌድ ለ5ተኛ ዙር እግረኛ ተዋጊዉችን አሰልጥኖ ማስመረቁን የሕዝብ ግንኙነቱ ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል!

በትላንትናው ዕለት ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ኮማንዶ እና እግረኛ ተዋጊዎችን ለበርካታ ወራቶች ካሰለጠነ በኋላ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች አርበኛ ሀብቴ ወልዴ የዕዙ ዋና አዛዥ፣ አርበኛ ተሾመ አበባዉ የዕዙ ም/ል አዛዥ፣ አርበኛ ደረጀ በላይ የዕዙ ዘመቻ መምሪያ ሀላፊ፣ አርበኛ ፀዳሉ ደሴ የዕዙ ስልጠና ዘርፍ ሀላፊ፣ ብ/ጄኔራል ተዘራ ንጉሴ፣ አርበኛ ሸርብ አቸነፍ እና በርካታ እንግዶች እንዲሁም የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች የነብሮ ብርጌድ እና ዳግማዊ ቴድሮስ ብርጌድ አመራሮች ፣ የኪነ ጥብብ ባለሞያዎች በተገኙበት በደማቅ ማስመረቁን ለኢትዮ 251 ሚዲያ የቋራ ኦሜድላ ክፍለጦር ገልጸዋል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

03 Nov, 15:14


ሰበር ዜና!

በአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ክፍለጦር ልዩ ኦፕሬሽናል ቡድን በቁጥጥር ስር የዋለው የ105ኛ ክፍለጦር የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ከብዙ ሰነዶች ጋር እንደተያዘ ተገለፀ።

በእነዋሪ የተፈፀመውን ጥቃት ጨምሮ በሸዋ ቀጠና በርካታ የአገዛዙ ኦፕሬሽኖችን ሲመራና ሲያስተባብር የነበረው የ105ኛ ክፍለጦር ልዩ ዘመቻ መሪና የሰሜን ሸዋ ዞን ኮማንድ ፖስት የመረጃ ክፍል መቶ አለቃ አማረ በአርበኛ መከታው ማሞ በሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ክፍለ ጦር ልዩ ኦፕሬሽናል ኃይል መያዙን ገልፀን የነበረ ሲሆን ዝርዝር መረጃው አሁን ደርሶናል።

አገዛዙን ከድተው የፋኖ ሃይልን ከሚቀላቀሉት ባሻገር በዕዙና በስሩ በሚገኙ ክፍለጦሮች ልዩ ኦፕሬሽናል ቡድን በርካታ የአገዛዙ ሃይሎች በቁጥጥር ስር እየዋሉ እንደሚገኙም ታውቋል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አርበኛ አበበ ሙላት ለኢትዮ 251 ሚዲያ እንደገለፀው በቁጥጥር ስር በዋለው የብልፅግና ሠራዊት ከፍተኛ አመራር መቶ አለቃ አማረ እጅ ላይ የአገዛዙን ገመና የሚገልጡ ወታደራዊ ሚስጥሮችን ጨምሮ በንፁሃን ላይ ጭፍጨፋ የሚፈፀሙበት የሰነድ ማስረጃ ማግኘታቸውን ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

02 Nov, 16:06


https://youtube.com/live/DTsVDoqaE6Y?feature=share

Ethio 251 Media

02 Nov, 11:59


የአማራ ፋኖ ነፃ ባወጣቸው ቀጠናዎች የሲቪል አስተዳደር ምስረታዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

ማህበረሰቡም ራሱ በመረጣቸው ሰዎች እንዲተዳደር መደረጉም ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የአምስተኛ ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ፋኖ ደሳለው ሙሉጌታ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ያደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አባቡ አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

02 Nov, 11:20


የአማራ ፋኖ በጎጃም በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች እያደረጋቸው ያሉ ትንቅንቆች ምን ይመስላሉ ?

የአገዛዙ ሀይል በህዝብ ላይ እየፈፀመ የሚገኘው ጥፋትና ውድመት በምን ልክ ይገለጣል?

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ የአገዛዙ ሠራዊት እንቅስቃሴና የፋኖ ድሎችን በተመለከተ  ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

02 Nov, 11:12


የአማራ ፋኖ ከተጋድሎ ባሻገር ወታደራዊ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ይገኛል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም ስር የሚገኘው አብራጂት ብርጌድ የልዩ የኮማንዶ ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ የአብራጂት ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት መ/ር ደሳለኝ ወርቄ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በሰጠው ቃለምልልስ ገልጿል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

02 Nov, 11:00


የአማራ ፋኖ ማህበራዊ ተሳትፎ የደረሱ ሰብሎችን በመሰብሰብ ቀጥሏል።

የአማራ ፋኖ በወሎ የላስታ አሳምነው ኮር የእሸት ክፍለ ጦር የደረሱ ሰብሎችን እየሰበሰበ ይገኛል።

ጋዜጠኛ ደረበ መኮንን ለኢትዮ 251 ያደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

02 Nov, 10:36


በወሎ ቀጠና ተጋድሎዎች ቀጥለዋል።

ሁለንተናዊ ሽንፈት የደረሰበት አገዛዙ የአውደ ውጊያ ሽንፈቱን በአዳራሽ ፕሮፖጋንዳ ለመቀልበስ ቢሞክርም ከሽፎበታል።

የአማራ ፋኖ በወሎ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።


https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

02 Nov, 08:58


ጥብቅ የጥንቃቄ መረጃ

የብልፅግና አገዛዝ የ2 ወር የጦርነት እንዲሁም የጥፋት እቅዶችና አካሄዶች ምን ይመስላሉ ?

የደብረዘይቱ የከፍተኛ መኮንኖች ባደረጉት ስብሰባ ቮልኮ የወጣው ሚስጥራዊ  መረጃ !

ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን ሚስጥራዊ መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር እንደሚከተለው አቅርቦታል ።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Nov, 19:06


ወሎ ቤተ -አምሃራ

የአማራ ፋኖ በወሎ በቀጠለዉ የህልዉና ተጋድሎ

በአርበኛ እንድሪስ ጉደሌ የሚመራዉ የጊራና ባለሽርጡ ክ/ር በጊራና ልዩ ቦታዉ ፋጅ ተብሎ በሚጠራዉ የቱርክ ካምፕ ላይ መሽጎ የከረመዉ የአብይ ወንበር አስጠባቂ ሰራዊት ንጋት 11 ሰአት ላይ ምሽጉን ለቆ ለቅኝት በወጣበት ሰዐት :ለብዙ ቀናቶች ባለመሰልቸት የደፈጣ ቦታ በመያዝ በደፈጣ ለመምታት ሲጠባበቁ በነበሩት የባለሽርጡ የሶስተኛ ሻለቃ ፋኖዎች ባደረሱበት የደፈጣ ጥቃት
ከ8 በላይ የጠላት ሀይል ሲደመሰስ በ4ባጃጅ ቁስለኛ ሲያመላልስ ዉሏል።

በዚህ መብረቃዊ ጥቃት የተበሳጨዉ አራዊቱ የአብይ አህመድ ሰራዊት የዉርዴቱ ማካካሻ የሆነዉን የሲቪሊያን ግድያ ልምዱን በስፋራዉ ግመል ሲጠብቅ የነበረዉን ሀብታሙ የተባለ ወጣት በጥይት ደብድቦ ገድሏል።

ህዝባችን ይህን ጣረ ሞት ላይ ያለ ፀረ አማራ ስርአት ላንዴና ለመጨረሻ ለመቅበር በምናደርገዉ የህልዉና ትግል ዉስጥ በመቀላቀል አማራዊ ግዴታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን ።

ድል ለፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ጥቅምት 22/2017 ዓ.ም

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Nov, 18:24


በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ደራ አካባቢ በኦነግ ሸኔ ታግተው የነበሩት የመስጅድ ኢማም ከ12 ቤተሰቦቻቸው ጋር መገደላቸው ተሰማ‼️

በደራ ወረዳ ገንዳ አረቦ ተብሎ በሚጣራው አካባቢ ከሀጂ አህመድ መስጅድ በታጣቂዎች ታግተው የነበሩት የሀጂ አህመድ መስጅድ ኢማም ሼይኽ ሙሀመድ መኪን ሸይኽ ሙሀመድ አሪፍ አብረዋቸው ታግተው ከነበሩት 12 ቤተሰቦቻቸው ጋር በዛሬው ዕለት መገደላቸው ተሰምቷል።

ሼይኽ ሙሀመድ ከሳምንታት በፊት የሱብኺ ሶላት አሰግደው በሚመለሱበት ወቅት ነበር ቤተሰቦቻቸውን ጨምሮ ከ30 በላይ የሚሆኑ የአካባቢው ሰዎች ታግተው በሸኔ ሀይሎች መወሰዳቸው የተገለፀው። ከቀናት በኋላ በተደረገ የገንዘብ ድርድር የኢማሙን እናት እና ባለቤት ጨምሮ ጥቂት ሰዎች መለቀቃቸው የተገለፀ ሲሆን ኢማሙን ጨምሮ 12 ቤተሰቦቻቸው በዛሬው እለት መገደላቸው ተሰምቷል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Nov, 16:33


https://youtube.com/live/tY3e7r2XS2E?feature=share

Ethio 251 Media

01 Nov, 16:06


70 ይቀራል!

የአሁን መግቢያ ነው። በፍጥነት 1000 ሰብስክራይብ እንሙላው

https://www.youtube.com/@ETHIO251MEDIA67

Ethio 251 Media

01 Nov, 10:25


ጥብቅ የጥንቃቄ መረጃ

የብልፅግና አገዛዝ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ ያካሄደው ስብሰባ ከሽፎበታል።

የአብይ አህመድ ብልፅግና በአውደውጊያ የተወሰደበትን ብልጫ በአዳራሽ ፕሮፖጋንዳ ሊያጨበረብር ቢሞክርም የህዝቡ ምላሽ አስደንጋጭ ሆኖበታል።

ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን ጥብቅና ሚስጥራዊ መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር እንደሚከተለው አቅርቦታል ።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Nov, 09:42


የአገዛዙን አሁናዊ ሁኔታዎችን ፤ የክፍለጦሩ የተጋድሎ ውጤቶችን በተመለከተ:-

የአማራ ፋኖ በጎጃም የራስ ቢትወደድ መንገሻ አቲከም የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ደሳለው ሙሉጌታ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከተተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

01 Nov, 09:04


የአማራ ፋኖ በጎጃም የበላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር ክፍለ ጦር ሰብሳቢ ፋኖ በላይነህ ዋልተንጉስ ከዛምበረሃ ብርጌድ ፋኖ አባት ጋር ውይት አድርገዋል።

የክፍለጦሩ አዛዥ ከብርጌድ አመራሮች ጋር በነበራቸው ቆይታ የአደረጃጀት ግንባታና የግዳጅ አፈፃፀምን በተመለከተ ቆይታ አድርገዋል።

ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አባቡ አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 21:48


አሳዛኝ ዜና!

በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ በሸኔ ታጣቂዎች በደረሰ ጥቃት እስከ 40 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ።

ጥቃቱ የደረሰው በዞኑ የሶዶ ወረዳ ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሸዋ ዞን ዱግዳ ወረዳ ጋር በሚዋሰንበት አካባቢ ቢርቢርሳና ጋሌ ቀበሌ ልዩ ስሙ ''ኩሬ'' እንዲሁም ''ቢጢሲ'' ተብለው እስከሚጠሩ ስፍራዎች ነው።

በሸኔ ታጣቂዎች በደረሰው ጥቃት እስከ 40 ሰዎች መገደላቸውንና ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች መኖራቸውን ዛሬ ከስፍራው የደረሱን ተደጋጋሚ መረጃዎች አመላክተዋል።

ጥቃቱ ትላንት ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:00 ገደማ ጀምሮ እስከ እኩለ ለሊት መራዘሙን የጠቆሙት የአካባቢው ነዋሪዎችና የሟቾች ቤተሰቦች በጥቃቱ ሕጻናትን ጨምሮ እናቶችና አረጋውያን መገደላቸውንም ተናግረዋል።

የተከፈተባቸውን ጥቃት መመከት ያልቻሉ አርሶ-አደሮች ቤታቸው ውስጥ እያሉ በእሳት እንዲቃጠሉ በማድረግ ከነከብቶቻቸው እንዲሞቱ መደረጉንም ነዋሪዎች ገልፀዋል።

በአካባቢው የመንግሥት መዋቅሮች በኩል እስካሁን ስለጉዳዩ ግልፅ መረጃም ሆነ ድርጊቱን የሚያወግዝ መግለጫ አልተሰጠም።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 18:24


November 7, 2024

የአማራ ማህበር በሲያትል የተቃውሞ ሰልፍ ቀጠሮ ይዘዋል።

ሲያትል በአይነቱ ለየት ያለ የመኪና ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ተዘጋጅቷል !!

ያለ ልዩነት በጋራ ለአንድ ህዝብ ለአንድ ዓላማ አደባባዩን እናጥለቀልቀዋለን ብለዋል

ማስታወቂያውን ተመልከቱት !

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 17:56


የአማራ ፋኖ በወሎ አሳመነዉ ኮር እሸት ክ/ጦር ወታደራዊ አዛዥ የነበረዉ የሻለቃ ሰማኝ አማረ 40ኛ ቀን መታሰቢያ በዛሬዉ ዕለት ማለትም ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም በእሸት ክ/ጦር አመራሮች እና የፋኖ አባላት ታስቦ ዉሏል!!

ታጋይ ይሰዋል፣ ትግል ይቀጥላል!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 17:00


የአማራ ፋኖ በወሎ አሳመነዉ ኮር እሸት ክ/ጦር ወታደራዊ አዛዥ የነበረዉ የሻለቃ ሰማኝ አማረ 40ኛ ቀን መታሰቢያ በዛሬዉ ዕለት ማለትም ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም በእሸት ክ/ጦር አመራሮች እና የፋኖ አባላት ታስቦ ዉሏል!!

ታጋይ ይሰዋል፣ ትግል ይቀጥላል!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 16:06


https://rumble.com/v5kx35k--251-october-31-2024-251-zare-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

31 Oct, 15:49


700 ይቀራል

የአሁን መግቢያ ነው። በፍጥነት 1000 ሰብስክራይብ እንሙላው

https://www.youtube.com/@ETHIO251MEDIA67

Ethio 251 Media

31 Oct, 15:38


የምዕራብ ወሎ ኮር ምስረታን በተመለከተ ከአማራ ፋኖ በወሎ የተሰጠ መግለጫ

ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ/ም

የአማራ ፋኖ በወሎ ካሉት ክፍለ ጦሮች መካከል ከደሴ ከተማ በስተምዕራብ በኩል የሚንቀሳቀሱት 3 ክፍለ ጦሮች በአንድ ወታደራዊ ኮር እንዲታቀፉ መደረጉን ድርጅታችን እየገለጸ:-

1.  የንጉሥ ሚካኤል አሊ ክፍለ ጦር፣

2. የአማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር፣

እና

3. ቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር

ቀጠናዊ የክፍለ ጦር ለክፍለ ጦር ግንኙነታቸውን አጠናክረው በመቀጠል ግዳጅ የመፈጸም አቅማቸውን ማሳደግ እና የትግሉን ዙር ማክረር እንዲችሉ ማድረግ በማስፈለጉ የተነሳ በቀጠናው ያሉት እነዚህ 3 ክፍለ ጦሮች በአማራ ፋኖ በወሎ ስር ምዕራብ ወሎ ኮር በሚል ስያሜ ተደራጅተዋል::

ለዕዝ ሰንሰለት ስምረት እና ለአስተዳደራዊ አመችነት ሲባል ክፍለ ጦሮችን በኮር የማደራጀት እንቅስቃሴ ከተጀመረ የሰነበተ ሲሆን የአማራ ፋኖ በወሎ በያዘው እቅድ መሰረት የምዕራቡን ክፍል በኮር የማደራጀት ስራውን በዛሬው እለት አጠናቋል::

የምዕራብ ወሎ ኮር ከደሴ እስከ ሳይንት ጫፍ በሽሎ ወንዝ ድንበር ድረስ የሚያካልል የፋኖ ሀይልን ያቀፈ ሲሆን የአፄ ቴዎድሮስ አጽመ እርስት ከሚገኝበት መቅደላ አምባ እስከ ጌታው ሸህዬ ሀገር ደገር የሚዘረጋ ግዙፍ ኮር ነው:: ከሸዋ ድንበር በቶ እና ወለቃ ወንዞች እስከ ጎንደር ድንበር በሽሎ ወንዝ እንድሁም የጎጃም እና ወሎ መዘያየሪያ የሆነው አባይ ወንዝ ድልድይ ድረስ የሚወነጨፍ የፋኖ ሀይል በኮሩ ስር የተሰበሰበ ሲሆን የኮሩ መስራች የሆኑት 3 ክፍለ ጦሮች ያቀፏቸው ብርጌዶች፣ ሻለቃዎች እና ሻምበሎች ከምዕራብ ወሎ ቀጠና ባሻገር ወደ ጎንደር፣ ጎጃም እና ሸዋ በመወርወር ግዳጅ መወጣት እንደሚችሉ ተደርገው የተደራጁ መሆናቸውን እየገለፅን የቀጠናው ፋኖዎች ወንዝ ተሻግረው እና ጎራ ዙረው ግዳጅ ለመወጣት የሚያስችላቸውን ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ጭምር በቀኝ አዝማች ይታገሱ አራጋው ስም ሰይመው ለሰማዕተ ጓዳችን እና ወንድማችን ማስታወሻ የሚሆን የተቋም ሀውልት እንዲቆምለት ማድረግ ተችሏል::

የምዕራብ ወሎ ኮርን በዋና ሰብሳቢ/ዋና አዛዥ የሚመራው ስመጥሩው አርበኛ ሳጅን አደም አሊ (አባ ናደው) ሲሆን በጥብቅ ወታደራዊ ዲስፕሊን የታነፀ እና ግዳጅ የመፈፀም ብቃቱ አኩሪ መሆኑ የተረጋገጠ ሰራዊትን ያቀፈ ኮር ነው:: አርበኛ ሳጅን አደም አሊ ጋር ኮሩን በመምራት ትግሉን ወደተሻለ ምዕራፍ ያሸጋግራሉ ተብለው የታመነባቸው የኮሩ የስራ አስፈጻሚ አባላት ስም እና ኃላፊነት ዝርዝር መረጃ በቀጣይ ለታጋይ ሰራዊታችንና ለህዝባችን ይፋ የምናደርግና የምናሳውቅ ይሆናል::


ድል ለፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ጥቅምት 21/2017 ዓ.ም

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 12:22


የብልፅግና ወንበዴ  ቡድን የሁለት አመት ጨቅላ ህፃን ማገቱ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር ከፍተኛ አመራር የሆነው ፋኖ አቀናው በቀለ የትዳር አጋር የሆነችው ወ/ሮ ሃገሬ ዮሀንስ   ሸንፈቱን እየተከናነበ የሚገኘው የብልፅግና ሠራዊት ከጥቅምት 10/2017 ዓ.ም ጀምሮ በፌጥራ ከተማ የሁለት አመት ህፃን ልጇን ጨምሮ  አግቷት እንደሚገኝ ተገልጿል።

የታቀፈችውን ጨቅላ ህፃን እንደያዘች የታገተቸው እናት ከታገተችበት ቀን ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ  ያለችበት ሁኔታ እንደማይታወቅ ተገልጿል።

ተከታተሉት.....
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 12:13


የአማራ ፋኖ በጎጃም 1 ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ሙሉሰው የኔ አባትከ ኢትዮ 251 ሚዲያ ያደረሰውን ቃለ ምልልስ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አቅርቦታል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 12:04


የአማራ ፋኖ በጎጃም በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች እያደረጋቸው ያሉ ትንቅንቆች ምን ይመስላሉ ?

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ የአገዛዙ ሠራዊት እንቅስቃሴና የፋኖ ድሎችን በተመለከተ  ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 11:49


የወንበዴው ብልፅግና ሃይል በፋኖ የሚሰነዘርበትን በትር መቋቆም ሲሳነው የውሸት ዜና እያሰራጨ እንደሚገኝ ተገለፀ።

በአዲስ ቅዳም የሚገኙ የሚሊሻ አባላትን ትጥቅ ያስፈታው የአገዛዙ ሠራዊት ሀሰተኛ ዜና ለማሰራጨት ሊጠቀምባቸው እንደሆነም ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም 5ተኛ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ፋኖ ደሳለው ሙሉጌታ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

31 Oct, 09:54


በእስቴ ወረዳ ገንዳ ጠመም ቀበሌ 9 ሴቶች በአገዛዙ ሠራዊት አባላት መደፈራቸው ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክፍለ ጦር እስቴ ደንሳ ብርጌድ በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች፤ በእስቴ ወረዳ መካነእየሱ ከተማ የትምህርት አገልግሎት ማስጀመሩንም ገልጿል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር የጉና ክፈለጦር  የእስቴ ደንሳ ብርጌድ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ማረው ክንዱ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ያደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ እንበርብር አቅርቦታል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

30 Oct, 18:13


የአገዛዙ ጭካኔ!

ሃገሬ ዮሀንስ ትባላለች፣ የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር ከፍተኛ አመራር የሆነው ፋኖ አቀናው በቀለ ባለቤት ስትሆን ሸንፈቱን እየተከናነበ የሚገኘው የብልፅግና አራዊት ሰራዊት ከጥቅምት 10/2017ዓ.ም ጀምሮ በፌጥራ ከተማ የሁለት አመት ህፃን ጨምሮ አግቷት ይገኛል።

ከታገተችበት ቀን ጀምሮእስከ አሁን ድረስ ከነ ህፃኗ ያለችበት ሁኔታ የታወቀ ነገር የለም ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለጦር ሚዲያና ኮምንኬሽን ተጠሪ ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

30 Oct, 16:52


ሰበር ዜና!

የአማራ ፋኖ በወሎ አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር ክንፍ የሆነው በመሃል ሳይንት ወረዳ የሚንቀሳቀሰው በፋኖ ጎሹ ሳይንቴው የሚመራው አትሮንስ ብርጌድ ዛሬ  አመሻሽ ላይ  11:40 አካባቢ ማለትም ዕሮብ 20/2017 ዓ/ም  ወደ ወረዳው መቀመጫ ወደሆነችው ደንሳ ከተማ ሰርገው በመግባት ልዩ ኦፕሬሽን መስራታቸው ተገልጿል።

በዚህም ኦፕሬሽን  በአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበ ሲሆን  አቶ አስሜ በላቸው ከ039 አህዮ ቀበሌ የዘለቀ ሆድ አደር ሚሊሻ  እና ከ042 ቀበሌ ዋጩ ቀጠና  የዘለቀ ስንደው የሚባሉ  ሁለት  ሚሊሾች ላይመለሱ ተሸኝተዋል ሲል የአትሮንስ ብርጌድ ዋና አዛዥ  ፋኖ ጎሹ ሳይንቴው ገልጿል።

የተቀረው በፍርሃት ቆፈን የገባው ጥምር ጦር የሞቱትን አስከሬን ሳያነሳ ግማሽ ከተማን ለጀግኖች አስረክቦ ወደ ካምፕ ፈርጥጦ ገብቷል ሲሉ የመረጃ ምንጮች አሳውቀዋል። 

የጀግኖችን ክንድ መቋቋም ያቃተው የብርሃኑ ጁላ ግሪሳ ሰራዊት ወደካምፕ ገብቶ አሁን በዚህ ስዓት ሞርተር እየተኮሰ ማህበረሰቡን እያሸበረ ይገኛል ሲሉ ምንጮች አክለው ገልፀዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

30 Oct, 16:37


https://rumble.com/v5kqyal--october-30-2024-251-zare-ethio-251-zare.html

Ethio 251 Media

30 Oct, 16:31


https://x.com/251media/status/1851661066364928166?s=46

Ethio 251 Media

30 Oct, 14:14


ሰበር የድል ዜና
//
የአማራ ፋኖ በጎጃም በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ንጉስ ተክለ ሐይማኖት ብርጌድን እይዛለሁ ብሎ ከደብረ ማርቆስና ከረቡ ገበያ የወጣው የጠላት ኃይል ባላሰበው መንገድ ገብቶ እየተቀጠቀጠ ነው።
በውጊያው የሶስት ክፍለ ጦር የፋኖ አባላት ታሪክ እየፃፉ ነው።በዚህ ታሪካዊ ጠላትን የመደምሰስ ተጋድሎ ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ክፍለ ጦር፣በላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር፣ሐዲስ አለማየሁ ክፍለ ጦር እንዲሁም ሌሎች አጎራባች ወረዳ ያሉ ብርጌዶች እየተሳተፉበት በሚገኘው በዚህ አውደ ውጊያ ጠላት ዳግም ወደ ጮቄ ማሰብ አድለም ቃሉን እንዳይጠራ የሚደረግበት ውጊያ ነው።
ዛሬ ለጆሮ የሚደንቅ የብስራት ዜና ከሰዓታት በኃላ እናበስራለን።
በተረጋጋ መንፈስ ጠብቁን ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን!!
መልክት፦
የፋኖን በትር መሸከም ያቃተው በየሰፈሩ የሚገኘውን ንፁህ አርሶ አደር እንዲሁም በየቦታው ያገኘውን ወንድ ልጅ ሁሉ እየረሸነ ነው።ንፁሐንን ረሸነ ብለን ጠላትን ከመደምሰስ ግን የሚያግደን ምድራዊ ኃይል የለም።
አዲስ አብዮት
አዲስ ድል
አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
በወንበዴዎች ወንበር የማይናውዝ አዲስ ትውልድ በክንዳችን እና በአንደበታችን እንፈጥራለን።
የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ አርበኛ

መ/ር ታደገ ይሁኔ(ሸርብ)

Ethio 251 Media

30 Oct, 13:37


ሰበር የድል ዜና!

በሁለት አቅጣጫ ወደ ፋኖ ያመራው ወራሪው የምርኮኛው ብርሀኑ ጁላ የመከላከያ አራዊት ሰራዊት ቡድን በአናብስቶቹ እርምጃ ተወሰደበት።

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ ወደ ሚዳ ወረዳ ተጨማሪ ወራሪ ሀይል ለማስገባት በተደረገው እንቅስቃሴ ዛሬ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 12:30 እስከ ቀኑ 7:30 ድረስ የሸዋ አናብስቶች የአርበኛ መከታው ሞሞ ልጆች ወራሪውን የጠላት ሀይል ሲያስጨንኩት መዋላቸውን ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።

በዚህ ድንቅ ኦፕሬሽን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር በፋኖ ሞገስ መስፍን የሚመራው የቀስተ ንህብ ብርጌድ እና በፋኖ መንፈስ ፀጋው የሚመራው የክፍለ ጦሩ ልዩ ተወርዋሪ ጦር ባደረጉት አውደ ውጊያ ጠላት ከፍተኛ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ደርሶበታል።

መነሻውን አለም ከተማ ያደረገው የወራሪው ሀይል ተጨማሪ ሀይል ወደ ሚዳ ወረዳ ለማስገባት ባደረገው እንቅስቃሴ በአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ልዩ ተወርዋሪ ዘመቻ በንስሮቹ አይን ላይ የወደቀው የጠላት ሀይል ከዋሶ ጨበሬ እስከ ጨለሚት ድረስ ሲገረፍ ውሏል።

በሌላኛው አቅጣጫ የመጣውን የጠላት ሀይል ለመቀበል እና ሽፋን ለመስጠት መነሻውን መራኛ ከተማ ያደረገው የምርኮኛው ብርሀኑ ጁላ ሰራዊት በቀስተ ንህብ ብርጌድ አባላት በ "በግ ስርጥ" እና በ "ሾላ ሜዳ " አቅጣጫ በክንደ ነበልባሎቹ የደፈጣ ጥቃት ተፈፅሞበታል።

ዛሬ በተካኼደው አውደ ውጊያ በጠላት ሀይል ላይ ከፍተኛ አካላዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ሲደርስበት፣ ወራሪው ሀይል ከባድ ቁስለኛውን ወደ ጃሞ ደጎሎ ሆስፒታል የጫነ ሲሆን ፤ ቀላል ቁስለኛውን መራኛ ከተማ በሚገኘው ሆስፒታል ማስገባቱን የውስጥ አርበኞቻችን መረጃውን አድርሰውናል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ዶ/ር ፋኖ አበበ አላዩ ለኢትዮ 251 ሚዲያ አስታውቋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃት አንደበት !

   https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Oct, 20:21


ፋኖ ዶ/ር አቡበክር ሰኢድ ከመረብ ሚዲያ ጋር!

የትግል ጓዶቹ "እጁ ፈዋሽ ነው" ይሉታል። ዶ/ር አቡበክር የነካቸው ቁስለኞች አፍታ ሳይቆዩ ይፈወሳሉ።

ዶ/ር አቡበክር ከሕክምና ባለሙያነቱ ጎን ለጎን ስናይፐር፣ አር ፒጂ፣ ኤኬ 47 እና ዲሽቃ ይተኩሳል።

ከህክምናው ጎን ለጎን በውጊያ ወቅት ክፍት በሆኑ ቦታዎች በመግባት ይዋጋል።በውጊያ ወቅት በተደጋጋሚ ተቆርጦ ከበባ ውስጥ የገባ ቢሆንም ነገር ግን ከሃኪምነቱ በተጨማሪ ወታደራዊ ልምድ ስላለው ከበባውን ሰብሮ ለመውጣት ችሏል።

ዶ/ር አቡበክር ከጣቢያችን ጋር ባደረገው ቆይታ፦

👉 አገዛዙ ማሕበረሰቡ ሕክምና እንዳያገኝ የጤና ተቋማትን ማውደምን፣ የጤና ባለሙያዎችን መግደልንና ማሰርን እንዲሁም መድሃኒት መከልከልን ልክ እንደ አንድ የጦር መሣሪያ እየተጠቀመ ስለመሆኑ

👉ከውጊያው ጎን ለጎን በሕክምና ዘርፉ ስለሚደረጉ ተጋድሎዎች

👉 በወቅታዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች

👉አጠቃላይ ስለ ትግሉ ሁለንተናዊ ሁኔታ እና ሌሎች ሃሳቦችም ተነስተዋል።

ይከታተሉ👉https://www.youtube.com/watch?v=ROQhxNIG_Ms

Ethio 251 Media

29 Oct, 16:38


https://www.youtube.com/live/WB4S0A0-_PQ?feature=shared

Ethio 251 Media

29 Oct, 15:38


ሰበር ዜና!

የ105ኛ ክፍለጦር የዘመቻ መምሪያ ኃላፊ በሸዋ ቀጠና በቁጥጥር ስር ውሏል!

በእነዋሪ የተፈፀመውን ጥቃት ጨምሮ በሸዋ ቀጠና በርካታ የአገዛዙ ኦፕሬሽኖችን ሲመራና ሲያስተባብር የነበረው የ105ኛ ክፍለጦር ልዩ ዘመቻ መሪና የሰሜን ሸዋ ዞን ኮማንድ ፖስት የመረጃ ክፍል መቶ አለቃ አማረ በአርበኛ መከታው ማሞ በሚመራው የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ መሀመድ ቢሆነኝ ክፍለ ጦር ልዩ ኦፕሬሽናል ኃይል መያዙን ከክፍለጦር አመራሮቹ ኢትዮ 251 ሚዲያ አረጋግጣለች።

ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Oct, 15:32


ሰበር ዜና!

አንዳቤት ብርጌድ ከጣና ገላውዲወስ ክ/ለጦር ጋር በጥምረት በገላውዲወስ፣ በልጫ፣ በጅብ አስራ እስቴ ዴንሳ ብርጌድ ከሀገረ ቢዘን ብርጌድ ጋር በጋሳይ፣ በልዋየ በኩል ታላቅ ጀብድ ፈፅመዋል።

ሀገረ ቢዘን ብርጌድ ከገብርየ ክ/ለ ጦር እና ከራስ ጉና ብርጌድ ጋር በክምር ድንጋይ፣ በጓሳው በጥምረት የብልፅግና ስብስብን በሚገባ ገርፈውታል፣ ገብረ መስቀል ብርጌድ በደብታቦር፣ በአለም ሳጋ ፣ መቅደላ ብርጌድ በጋሳይ፣ በዘበራ መሀል መግባት ታላቅ የጀግንት አስተዋፅኦ አበርክታለች።

ሰሞኑን ከፍተኛ የሆነ የኃይል ክምችት በደቡብ ጎንደር ያደረገው የፋሽስቱ ስርዓት በጄ/ባንዳ /ማህመድ ተሰማ እንዲመራ በማድረግ ከፍተኛ የሆነ የንፁሀን ጭፍጨፋ፣ የንፁሀን ሀብት ዝርፊያን ተያየሰዝታል፣ በርካታ የአ/ርሶ አደሮችን የደረሰ ሰብል በሞርተር፣ በጄነራል መድፍ አቃጥሏል፣ የዞኑ ባንዳ አመራሮች በርካታ ንፁሀንን ለማስገደል አሳልፈው በስም ዝርዝር ለፋሽስቱ ሰጥተዋል፣ ስለዚህ ሁሉም የከተማ ነዋሪ እንደ አ/ርስ አደሩ በነቂስ ወጥቶ እራሱን ማዳን አለበት ሲል የአማራ ፋኖ በጎንደር የማህበራዊ ዘርፍ ኃላፊ እና የጉና ክ/ለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ምህረት አሳየ ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መልዕክት ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Oct, 15:14


የቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ የዕረፍት መታሰቢያ በዓል ዛሬ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም በአማራ ፋኖ በወሎ አሳመነዉ ኮር አማካኝነት ያለምንም የፀጥታ ችግር በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ ዉሏል።

ዝርዝር መረጃ አለው፤ በ251 ዛሬ ዝግጅታችን ይጠብቁን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Oct, 14:29


ሰበር የድል ዜና!!

በሁለት አቅጣጫ የመጣው የአገዛዙ ወራሪ ሰራዊት ከፍተኛ ጉዳት ደረሰበት!!

የአማራ ፋኖ በወሎ አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለጦር አካል የሆነው በተንታ ወረዳ የሚንቀሳቀሰው በፋኖ ሰይድ አለምዬ  የሚመራው ቴዎድሮስ ሻለቃን ለማፈን   ከመቅደለ ወረዳ እና ከተንታ ወረዳ በመነሳት  በሁለት አቅጣጫ ፋኖዎች ይገኙበታል፤ ወዳሉበት ቦታ የወተት 010 ቀበሌ ላይ በመሄድ ተኩስ የከፈተው የአገዛዙ አራዊት ሰራዊት ጥምር ጦር  ከጠዋቱ 12:00 ሰአት  እስከ ረፋዱ 5:00 ሰአት ድረስ ከፍተኛ ትንቅንቅ የተደረገ ሲሆን በዚህም አውደ ውጊያ ላይ የአገዛዙ ጥምር ጦር  ከፍተኛ ጉዳትን አስተናግዷል። 

ከተንታ ወረዳ የመጡት የብርሃኑ ጁላ ጥምር ኃይል 3 ሙት እና  ከ5 በላይ ቀላልና ከባድ ቁስለኛውን ጭኖ ወደ መጣበት የተለመሰ ሲሆን፤ በተመሳሳይ ከመቅደላ ወረዳ የመጣው ጥምር ጦር ደግሞ ከፍተኛ  ጉዳት የደረሰበት ሲሆን ነገር ግን የደረሰበትን የጉዳት መጠን በውል ማወቅ ባይቻልም፤ ከአካባቢው ባገኘነው መረጃ መሰረት "እኛ ጉዳት ደርሶብን ወደኋላ አንመለስም የወንድሞቻችንን  ደም መመለስ አለብን" በማለት ተፋጠው እንዳሉና አመቻችተው ለማጥቃት እንዳሰቡ ምንጮች አክለው ገልፀዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Oct, 14:21


ሰበር ዜና!

አገዛዙን አወግዛው ለወጡ የመከላከያ አባላት የአማራ ፋኖ በጎጃም ቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ (6) ኛ ክ/ጦር የኢንጂነር ክበር ተመስገን ብርጌድ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አደረጉላቸው።

የአማራ ፋኖ  በውጊያም ሆነ በፖለቲካ አሉ ከሚባሉ ጠንካራ እና ብቁ ከሆኑ ብርጌዶች መካከል የኢንጂነር ክበር ተመስገን ብርጌድ በደምበጫ በዋናነት ይጠቀሳል። ምንም እንኳን የብልፅግና ካድሬዎች  የደምበጫን ፋኖ ለመበተን ከውስጥ እስከ ውጭ እጃቸውን ዘርግተው ቢንቀሳቀሱም የኢንጂነር ክበር ተመስገን የአደራ ልጆች የልዑል፣ የሽታሁን፣ የመምህር ላቃቸው የቃል ኪዳን ጓዶች በበሳል አመራር እና እንደብረት ተቀጥቅጠው ቀልጠው ጠንክረው የተደራጁ አባላት የእዝ ሠንሠለታቸውን እያጠናቅሩ ልዩነታቸውን በማጥበብ  የጠላትን ጎሮሮ እያነቁ ይገኛሉ።

በልዩነት ውስጥ መግባባት አለ የአስተሰሰብ እንጂ የአላማ ልዩነት እንደሌለ የገባቸው የብልፅግና ካድሬ እና ዙፋን ጠባቂ ሠራዊት አገዛዙን በመናቅ በአራቱም አቅጣጫ በግፍ እየወጡ ይገኛሉ፡፡ በዚህ ወር ብቻ በደምበጫ ወረዳ 11 መከላከያ 6 አድማ በትን 1 ፖሊስ እና 3 የሚልሻ አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው የኢንጂነር ክበር ተመስገን ብርጌድ አባላትን ተቀላቅለዋል::

ድል ለፋኖ ድል ለአማራ ህዝብ ድል ለተገፉ ኢትዮጵያውያን

ሪፓርተር ፋኖ ኃ/ ማርያም ተፈራ ከግንባር

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

29 Oct, 12:23


የአማራ ፋኖ በጎጃም በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች እያደረጋቸው ያሉ ትንቅንቆች ምን ይመስላሉ ?

የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ የአገዛዙ ሠራዊት እንቅስቃሴና የፋኖ ድሎችን በተመለከተ  ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

25 Oct, 20:55


የብልጽግና ሰራዊት በገፍ እየተማረከ ነው። ሙሉ ቪዲዮውን ይዘን እንመለሳለን...

Ethio 251 Media

25 Oct, 18:35


አገዛዙ ንፁሀን ላይ የሚያደርሰውን ጭፍጨፋ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ የተዘጋጀውን የትዊተር #Campaign ይቀላቀሉ።

https://linktr.ee/DigitalFano

Ethio 251 Media

25 Oct, 18:15


https://youtube.com/live/f3UEoCAUA8M?feature=share

Ethio 251 Media

25 Oct, 16:49


https://rumble.com/v5k3bvx--october-25-2024-251-zare-ethio-251-media.html

Ethio 251 Media

25 Oct, 16:05


https://www.youtube.com/live/S5766X9Mc4A?feature=shared

Ethio 251 Media

25 Oct, 12:34


የግፍ ተገፋዩ ህፃን !

ህፃን ዳዊት መካሽ ይባላል። ትላንት ጨፋጫፊው አብይ አህመድ በሸዋ-ይፋት-ራሳ-ሰፊበረት ቀበሌ በድሮን የገደለው ታዳጊ ምስል ይህ ነው።

Ethio 251 Media

25 Oct, 11:56


በጎጃም ቀጠና ያሉ አሁናዊ ሁኔታዎች ምን ይመስላሉ ?  የብልፅግናው አገዛዝ በተቋማት ላይ ውድመትና ጥፋት እየፈፀመ መሆኑ ሲገለፅ የግንባር ተጋድሎዎችም ቀጥለዋል።

በቀጠናው ያሉ ተጋድሎዎችና የአገዛዙ የጥፋት ስምሪትን በተመለከተ የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

25 Oct, 10:55


የእናት ፓርቲ መግለጫ!

በአዲስ አበባና በዙሪያዋ ሊፈርሱ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ቤተ እምነቶች !

አብያተ እምነት የሰማያዊ መንግሥት ተልዕኮ ማስፈጻሚያ ኤምባሲዎች በመሆናቸው ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል!
  
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠውን መግለጫ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አባቡ እንደሚከተለው አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

25 Oct, 10:25


ታላቅ አለም አቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ ለአማራና የአማራ ደጋፊዎች በሙሉ!

ጨፍጫፊው እና ፋሺስቱ የአብይ አህመድ አንባገነን አገዛዝ: በአማራ ህዝባችን ላይ
ጦርነት በማወጅ፣ በአሁኑ ሰዓት በሰውአልባ፣ በጦር አውሮፕላን እና በከባድ መሳሪያ በመታገዝ: የሚፈፀመውን የጅምላ ዘር ጭፍጨፋ በመቃወም በመላዉ ዓለም ለወገኖቻችን ድምፅ ለመሆን!

ሰልፉ የሚደረግባቸው የዓለም ከተሞች ፣

1. Berlin, Germany: Oct 18
2. Indianapolis, USA: Oct 25
3. ⁠Denver,USA: Oct 28
4. ⁠Seattle, USA: Nov 7
5. ⁠Frankfurt, Germany: Nov 9
6. ⁠Paris, France: Nov 9
7. ⁠Stockholm, Sweden: Nov 9
8. ⁠Queensland, Australia: Nov 9
9. ⁠Chicago, USA: Nov 9
10. ⁠London, UK: Nov 10
11. Washington, D.C., USA: Nov 10
112. Pretoria, South Africa: Nov 10
13. Minnesota, USA: Nov 10
14. Brussels, Belgium: Nov 10
15. Geneva, Switzerland: Nov 12
16. Oslo, Norway: Nov 23

Ethio 251 Media

25 Oct, 10:22


አጫጭር የግንባር መረጃዎች

ጎንደር ፣ጎጃም ፣ሸዋ እና ወሎ ቀጠናዎች የተደረጉ የግንባር መረጃዎች በጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር ይቀርባሉ።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

25 Oct, 10:06


የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ የዞብል ጃኖ ክፍለጦር ዋና አዛዥ ፋኖ ሸርብ እና ቃል አቀባዩ ወልደ ገብርኤል ሸርብ የጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።

አጠቃላይ ሁነቱን በተመለከተ የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ቋራ ኦሜድላ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ያደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

25 Oct, 08:43


በመንዝና በይፋት ቀጠና ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጉን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ገለፀ።

አስቴጎማ ክፍለ ጦር፣ መሃመድ ቢሆነኝ ክፍለ ጦር እና ምኒልክ ክፍለ ጦር በታጋድሎው ተሳትፎ በማድረግ ድል ማስመዝገባቸውም ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ፋኖ ስንታየሁ ደመቀ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

25 Oct, 06:47


የወልዲያ ሰርጅካል ኦፕሬሽን!

ጥቅምት 15 ቀን 2017 ዓ.ም
ኢትዮ 251 ሚዲያ

የአማራ ፋኖ በወሎ ወልድያ ከተማ ላይ ታላቅ ጀብዱ ፈፅሞ አደረ!

በፋኖ አርበኛ ጌታሁን ሲሳይ የሚመራው ብ/ጀኔራል አሳምነው ፅጌ ክፍለጦር የሰሜን ወሎ ዞን መቀመጫ የሆነዉን ወልድያ ከተማ ከበባ ዉስጥ አስገብቶ ያለ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን ጥቅምት 14/2017 አ.ም ሃሙስ ለአርብ አጥቢያ አዳሩን ትላልቅ ጀብዶችን ፈፅሞ አድሮዋል::

መሃል ወልድያ ከተማ ፒያሳ ላል ሆቴልና ሌሎች ትላልቅ ሆቴሎች ለስብሰባ መጥተው የከተሙ የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ጥምር ሰራዊት አመራሮችና የፖለቲካ አመራሮች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ተፈፅሞ አድሮዋል:: ጥቃቱ አመራሮች ባረፉበት ሆቴል በመስኮት ጭምር ቦምብ እየተጣለ ያደረ ሲሆን በርካታ ሙትና ቁስለኛ እንዳለም የከተማው ነዋሪ የአይን እማኞች ተናግረዋል::

በተጋድሎው ምሽት ወልድያ ከተማ ይንቀሳቀስ የነበረው የጠላት አራዊት ሰራዊት ባላሰበበት በጀግኖቹ የዋርካው ምሬ ወዳጆ ልጆች የተረፈረፈ ሲሆን አንድ የአመራር ፓትሮል ከሰባት ጠላት ጋር ሙሉ ለሙሉ ተደምስሶዋል ወድሞዋል::
በተጨማሪም ማር ማቀነባበሪያ ከፍ ብሎ ያለ ምሽግ ላይ በርካታ አድማ ብተና ሙትና ቁስለኛ ሆኖዋል::

በትናትናው እለት በሌሎች ተጋድሎዎችም የአሳምነው ክፍለጦር ቃኝ አላዉሃ ወንዝ ላይ ጠላት ብዙ ሙትና ቁስለኛ የሆነበትን ጥቃት ፈፅማ ዉላለች ሲል የአሳምነው ክፍለጦር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ንጉስ አበራ ለኢትዮ 251 ሚዲያ አስታውቋል።

ጠላት ራያ ቆቦ ዞብልና ራማ አጠቃላይ ምስራቁን ክፍል ለከበባ በመካናይዝድና በአየር ሃይል የታገዘ ከባድ ዉጊያ ከፍቶ የነበረ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በፋኖ አርበኛ ዋሴ ከበደ የሚመራው ዞብል አምባ ክፍለጦር አንደኛ እና ሶስተኛ(ራያ) ሻለቆች በፋኖ ካሳ አበበ የሚመራው ሃውጃኖ ክፍለጦር ሶስተኛ (ንጉስ ቸኮለ) ሻለቃ በፋኖ መሃመድ ሞላ የሚመራው ዲቢና ወርቄ ባለሽርጡ ብርጌድ እንዲሁም በፋኖ ኮማንዶ ጌታቸው ሲሳይ የሚመራው ልዩ ዘመቻ ድንጋይ ቀበሌና ራማ ገብርኤል ላይ በርካታ የጠላት ሃይል ረፍርፈው ሙትና ቁስለኛ አድርገው አንድ ቲም ምርኮኞችን ይዘው ከበባዉን ሰብረዉታል::

ሃውጃኖ ክፍለጦር ራያ ቆቦ ጮቢ በር ጥቁር አስፓልቱን በመቆጣጠር የጠላት ሃይል የሰው ሃይልና የሎጅስቲክ እንቅስቃሴ እንዳይኖረው አድርገዉታል::

መዳረሻው ድልና ማሸነፍ የሆነው የህልዉና ተጋድሎ ይቀጥላል!

ድል ለፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

24 Oct, 20:35


ሰበር ዜና!

ወልዲያ ሰርጂካል ኦፕሬሽን!

ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓ.ም
(ኢትዮ 251 ሚዲያ)

የአማራ ፋኖ በወሎ አሳምነው ክፍለጦር በፋኖ ጌታሁን ሲሳይ እየተመራ በወልደያ ከተማ ሰርጅካል ኦፕሬሽን እየፈፀመ መሆኑን የክፍለጦሩ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ንጉሥ አበራ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ከምሽቱ 4:10 ላይ የተጀመረው ተጋድሎ እስካሁን ቀጥሎ ከፒያሳ እስከ ጎንደር በር ባለው ቀጣና ትንቅንቅ ላይ ይገኛሉ።

በሰርጂካል ኦፕሬሽኑ እስካሁን በአገዛዙ ሀይሎችና ሰራዊቱን በሚያንቀሳቅሱ ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት ያደረሱ ሲሆን በርካታ ድልና የተጋድሎ ውጤቶችም ተጠባቂ እንደሆነ የክፍለጦሩ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ንጉሥ አበራ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጧል።

በወልደያ ከተማ ወልደያ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ለ12 ቀን የሚቀጥል የዞንና የወረዳ አመራሮች የብልጽግና ስብሰባ እያካሄዱ መሆኑ ይታወቃል።

ዝርዝር ዘገባ ይዘን እንመለሳለን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

24 Oct, 16:08


https://www.youtube.com/live/AKWZm1cWhRo?feature=shared

Ethio 251 Media

24 Oct, 15:15


አንድነት!

የደራ-ሸዋ ፋኖ አመራሮች ከአማራ ፋኖ በጎጃም አመራሮች ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ዉይይት አድርገዋል።

ወቅታዊ ፖለቲካዊና ወታደራዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረጋቸውን ኢትዮ 251 ሚዲያ ሰምታለች።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

24 Oct, 14:56


ሰበር ዜና!

የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በተኩስ እየተናጠ ነው።

ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓም ኢትዮ 251 ሚዲያ።

ይህ ዜና እየተጠናቀረ ባለበት ሰዓት ባህርዳር ከተማ ላይ የሚገኘው የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋና ጣቢያው በተኩስ እየተናጠ ነው።

የአማራ ፋኖ በጎጃም አንደኛ ክፍለ ጦር ባህርዳር ብርጌድ በላይ ሻለቃ በአሁኑ ሰዓት በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዋናው ጣቢያ ለይ የቦንብ ጥቃት መፈፀሙን ለኢትዮ 251 ሚዲያ አሳውቋል።

በዚህ ተቋም ላይ በፋኖ ሀይሎች የተፈፀመውን ጥቃት ተከትሎም የአገዛዙ ሀይሎች በንፁሀን መንደሮችና በባህርዳር ከተማ ባሉ በርካታ ትምህርት ቤቶች ላይ ጭምር  በህፃናትና ንፁሀን ላይ የቦንብ ጥቃቶችን እየፈፀመ እንዳለ የኢትዮ 251 ሚዲያ የመረጃ ምንንጮች ገልጠዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት !
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

24 Oct, 14:09


የዘጠኝና የስድስት ዓመት እህትማማቾች በአገዛዙ ተረሸኑ!

ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓ.ም
(ኢትዮ 251 ሚዲያ)

አገዛዙ ባደራጃቸው በባንዳው በካሪስ ጎቤ የሚመሩት የራያ ወርቄ ታጣቂዎች ዛሬ ጥቅምት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ራያ ቆቦ ወረዳ አዲስ አለም ቀበሌ ላይ ሁለት እህትማማች ህፃናቶችን በግፍ መረሸናቸውን የአይን እማኞች ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልፀዋል።

በአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀመ ካለው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ አራዊት ሰራዊት ጋር ወግነው ዘር ማጥፋት እየፈፀሙ ያሉት የራያ ወርቄ ታጣቂዎች ሃይማኖት ማርየ ሲሳይ የተባለች የዘጠኝ አመት እና ሳምራዊት ማርየ ሲሳይ የተባለች ስድስት አመት ህፃናት እህትማማቾች ደጃፋቸው ላይ በመጫወት ባሉበት ወቅት በአሰቃቂ ሁኔታ ግድያ መፈፀሙ ታውቋል።

ኦሮሚያ ወለጋና ደምቢደሎ አንሻ ሁሴንና መሰል ህፃናቶችን በግፍ ይረሽን የነበረዉና እየጨፈጨፈ ያለው የኦነግ ብልፅግና አራዊት ሰራዊት ዛሬም ከቀያችን ድረስ በመምጣት ባንዳዎችን በመመልመል እድሜና ፆታ ሳይገድበው ዘር ማጥፋት እየፈፀመ ይገኛል::

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!
https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 16:20


https://youtube.com/live/lO5ASsQKQE0?feature=share

Ethio 251 Media

22 Oct, 14:12


የንፁሀን ጭፍጨፋው ዓለም ዓቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ ጥሪ ቀረበ።

"በጎጃም ቀጠና የንጹሃን ጭፍጨፋ አሁንም እንደቀጠለ ነው፤ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ይህን ጉዳይ በትኩረት እንዲመለከተው ማሳሰብ እንፈልጋለን" አርበኛ ዝናቡ ልንገረው

በንፁሃን ላይ የሚደርስ የጭፍጨፋ ወንጀል አሳሳቢ መሆኑን የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል ሰብሳቢና ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ለኢትዮ 251 ሚዲያ በላከው መረጃ ገለጸ።

"በጎጃም ቀጠና ድጎ ፅዮን ቢቡኝ ወረዳ ወይንውሃ ከተማ የገባው የጠላት 72ኛ ክፍለጦር ህዝቡን በጅምላ እየሰበሰበ እየረሸነ ይገኛል፤ አርሶ አደሮችን እያገተ መሳሪያ አላችሁ አምጡ እያለ በሰውነታቸው ላይ ኮሸኮሽ እያንጠፈጠፈ የሌላቸውን ሰዎች ክላሽ ገዝተው እንዲያስገቡ በማድረግ ገዝተው ካስገቡ በኋላም እየተረሸኑ ይገኛሉ" ሲል የአማራ ፋኖ በጎጃም ወታደራዊ አዛዥ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

የወይን ውሃ ከተማ ነዋሪም ከተማውን ለቀው እየተሰደዱ ይገኛል። ይህ ሕዝብ በየቀኑ በጅምላ ከሚጨፈጨፍ ከፋኖ ጋር ተሰልፎ እንዲዋጋ እና ከሞት ራሱን እንዲያድን ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው ጥሪ አቅርቧል።

በቢቡኝ ዙሪያ ብቻ ከመስከረም 1 ቀን 2017 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም እስካሁን 30 የሚሆኑ ንፁሃን በአብይ አህመድ ተላላኪ ሰራዊት ተገድለዋል ያለው ዋና አዛዡ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው፤ ጎጃም ውስጥ እየተፈፀመ ያለው የንፁሃን ጭፍጨፋም የከፋ ሆኖ አግኝተነዋል ሲል ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 13:50


ሰበር ዜና

የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ ኃይል አምባ ጊዮርጊስ ላይ ድባቅ ተመታ!

በአርበኛ ሀብቴ ወልዴ የሚመራው የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ጎንደሬ በጋሻው ክፍለጦር ቴዎድሮስ ብርጌድ አሳምነው ሻለቃ፤ በፋኖ ወርቁ ዘገዬ እየተመራ አምባ ጊዮርጊስ ከተማ ዘልቆ በመግባት በርካታ ጀብዱዎችን መፈፀሙን ከዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ኢትዮ 251 ሚዲያ አረጋግጣለች።

አምባ ጊዮርጊስ ላይ በተደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ኪሳራ ሲደርስበት አማራ በመሆናቸው ብቻ የታሰሩ ንጹሃንን እስር ቤቱን በመስበር ማስፈታት መቻሉን ኢትዮ 251 ሚዲያ አረጋግጣለች።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ ጎንደሬ በጋሻው ክፍለጦር ቴዎድሮስ ብርጌድ አሳምነው ሻለቃ የጠላትን ኃይል ድባቅ የመታችው ሲሆን ከተማ ላይ የነበረው የብልጽግና ሰራዊት የፋኖን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው እየፈረጠጠ ካምፕ መግባቱን የጎንደሬ በጋሻው ክፍለጦር አመራሮች ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 13:09


በመንዝና ግሼ አውራጃ ባሉ ወረዳዎች፣ ቀበሌዎች፣ጎጦችና መንደሮች << ህዝባዊ አስተዳደር>> ማደራጀቱን እንደቀጠለ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ነፃ ባወጣቸው ቀጠናዎች ብልፅግናን አደረጃጀት እያፈረሰ፣ አማራዊ ቅርፅ ያለው ጊዜያዊ ህዝባዊ አስተዳደር መመስረት መቀጠሉንም ገልጿል።

በተለይ ህዝቡ ባሉት የማህበራዊ አገልግሎት ተቋማት እንዲገለገል፣ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ እንዲያዳብር እንዲሁም ለፋኖ ሁለንተናዊ ድጋፍ በማድረግ በነፃነት ለነፃነቱ  እንዲዋጋ በሰፊው እየተሰራም ይገኛል ሲል የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ገልጿል። 

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነፃነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 11:30


"የአማራ ዲያስፖራ ዓለም አቀፍ ጉባዔ  በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የጉባዔው ዋና ሰብሳቢ አምባሳደር ብርሃነመስቀል ነጋ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገለፁ።

በጉባኤው ላይ በዓለም ያሉ ከሰላሳ በላይ የአማራ ማህበራት፣ ምሁራንና በዘንድሮው የአሜሪካ ምርጫ የሚሳተፉ ተመራጮች መገኘታቸው ታውቋል።

እንደ አምባሳደር ብርሃነመስቀል ነጋ  ከአትዮ 251 ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታም በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት የምንሰራቸውን ዝርዝር ስራዎች በመግለጫ ይፋ እናደርጋለን ሲሉም ገልፀዋል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 10:48


አርበኛ ፋኖ ሞላ ደስዬ የጥቅምት ሰማዕት በሚል በትግል ጓዶቹ ታስቦ ውሏል።

አርበኛ ፋኖ መምህር ሞላ ደስየ የተሰዋህለትን አላማ ከግብ ለማድረስ የመጨረሻው ትንቅንቅ ላይ ነን:: ቃልህን ጠብቀን በድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን! ለድልም እንበቃለን ሲሉም የትግል ጓዶቹ አርበኛውን አስበውት ውለዋል።

ከትግል ጓደቹ ለኢትዮ 251 ሚዲያ የደረሰውን የመታሰቢያ መልዕክት ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር አቅርቦታል።

ክብር ዉድ ህይወታቸዉን ገብረው ለዛሬ ላደረሱን ሰማእቶቻችን!

https://t.me/ethio251media
  

Ethio 251 Media

22 Oct, 10:21


በጎንደር ቀጠና ጠላት ብልፅግና በልዩ ትኩረት ኢላማ አድርጎ ጥፋት በሚፈፅምባቸው አዲስ ዘመንና እብናት ለተከታታይ ቀናት በተደረገ ተጋድሎ በጎንደር ዕዝ ከፍተኛ ድል ተመዝግቧል።

የአማራ ፋኖ ጎንደር ዕዝ እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ መልካሙ ጣሴ በግንባር ተጋድሎና ድሎች ዙሪያ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 09:59


ዘመቻ ፲ አለቃ በሃይሉ በስኬት እየተጠናቀቀ እንደሚገኝና በደብረብርሃን ዙሪያ እና በሃገረማርያም ንፋስ አምባ በተባለ ቀበሌ ከፍተኛ ተጋድሎ መፈፀሙን የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ገለፀ።

በተለይ ደብረብርሃን ዙሪያ በተደረገው ተጋድሎ በጋራ ድል የተመዘገበበት እንደሆነም ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ንጋቱ ይታፈሩ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 09:42


በደራና ቀጠና እንዲሁም በደብረብርሃን ዙሪያ ከፍተኛ ተጋድሎ እያደረገ እንደሚገኝ የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ገለፀ።

በተለይ በደብረብርሃን ዙሪያ በተደረገው ተጋድሎ በጋራ ድል የተመዘገበበት መሆኑም ተገልፆል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ክፍል ፋኖ ስንታየሁ ደመቀ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 09:11


ሰበር ዜና!

ወልደያ ከተማ ላይ የአገዛዙ ሰራዊት በደፈጣ ተመታ!

ወልድያ ዙሪያ አሳምነው ክፍለጦር እያደረገ ያለው ተጋድሎ የቀጠለ ሲሆን ባህር ዳር መውጫ አፍሪኬር አካባቢ ጠላት ኬላ የሚያደርግበት ቦታ ላይ ደፈጣ በማድረግ የጠላት ኃይል ድባቅ መመታቱን የአማራ ፋኖ በወሎ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገለጸ።

የአገዛዙ ወንበር ጠባቂ ወታደር በደረሰበት ጥቃት ጠላት አምስት ሙትና ስድስት ቁስለኛ ያነሳ ሲሆን በወልድያና በሳንቃ በኩል ሁለት ዙ23 በማምጣት በዘፈቀደ እየተኮሰ ሲሆን ቃሊም መግቢያ አቦ ቤተ-ክርቲያን አካባቢ ሁለት እናቶችን በከባድ ሁኔታ ማቁሰሉን ገልጾ፤ አንደኛዋ እናታችን ወዲያውኑ ማረፋቸውን ፋኖ አበበ ፈንታው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

አገዛዙ አሁን ላይ ወደመጣበት የሸሸ ሲሆን ወልድያ ከተማ ተረጋግቶ መቀመጥና ስራ መስራት ስላልቻለ ራያ አላማጣ ያስቀመጠዉን ተጠባባቂ ቀይ ቆብ ለባሽ ፈርጣጭ ሰራዊቱን ዛሬ ያስገባ መሆኑን አረጋግጠናል፤ ቢሆንም ግን የሚያመጣው ለውጥ ስለማይኖር ተጋድሎዉ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የሕዝብ ግንኙነቱ ፋኖ አበበ ፈንታው ለጣቢያችን አስታውቋል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 09:02


የትግሉ ምዕራፍ እያደገ የፋኖ ስልጠናዎችና አዳዲስ ምሩቃኖችም ወደ ትግል እየተቀላቀሉ መሆናቸው ተገልጿል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የበላይ ዘለቀ ክፍለ ጦር የደባይ ጮቄ ብርጌድ አዳዲስ ምልምል ፋኖዎችን ማስመረቁን ለኢትዮ 251 ሚያ ባደረሰው መረጃ አሳውቋል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 08:42


ታላቅ ዓለም አቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ!
በ16 ከተሞች!

Ethio 251 Media

22 Oct, 08:42


በስንቅም በትጥቅም እየተደራጀ የሚገኘው የአማራ ፋኖ አዳዲስ ምልምል ኮማንዶ ፋኖዎችን እያስመረቀ ይገኛል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የተፈራ ዳምጤ ክፍለ ጦር ስር የሚገኘው የመብረቁ ተፈራ ብርጌድ ለ2ኛ ዙር የኮማንዶ ሃይሎችን ማስመረቁንም ለኢትዮ 251 ሚዲያ ባደረሰው መረጃ አስታውቋል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 08:28


በጎጃም ቀጠና ያሉ ተጋድሎዎችና የአገዛዙ ስምሪትን በተመለከተ የአማራ ፋኖ በጎጃም ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት.....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

22 Oct, 08:14


ከደብረማርቆስ ተነስቶ ወደ ረቡዕ ገበያ ሲንቀሳቀስ የነበረ የጠላት ሃይል በስናን አባጅሜ ብርጌድ የደፈጣ እርምጃ ተወስዶበታል።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ክፍለጦር የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ መምህር ታደገ ይሁኔ የግንባር ተጋድሎዎችን በተመለከተ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Oct, 18:02


★የድል ዜና

''ዘመቻ ፲ አለቃ በሀይሉ ሙሉጌታ''

በ ፲ አለቃ በሀይሉ ሙሉጌታ ተሰይሞ በሶስት የፋኖ ብርጌዶች እየተደረገ ባለው ዘመቻና የተጠናከረ ክንድ የተወቀጠው የመከላከያ ሰራዊት አንድ አይሱዙ ሙትና ቁስለኛ ተሸክሞ ፈረጠጠ::

በሀገረማርያም ከሰም ወረዳ ጥቅምት 11/2017 ከቀኑ 9:00 ጀምሮ በሦስት የውጊያ ግንባሮች ለተከታታይ ሶስት ሰዓታት በቆየ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ጀግናው የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ከሰም ክፍለጦር በጀግና ብርጌዶቹ ታላቅ ጀብዱን ፈፅሟል።

በከሰም ክፍለጦር ስር ከሚገኙት ከሀይለማርያም ማሞ ፣ከተስፋ ገብረስላሴ እና ከአስማረ ዳኘ ብርጌዶች የተውጣጡ ሻለቆች በአገዛዙ አጠራር በሸዋ ሀገረማርያም ከሰም ወረዳ ንፋስ አምባ፣መስኖ በር እና ሞዬ በተባሉ አቅጣጫዎች ከጠላት ጋር ባደረጉት መደበኛ ውጊያ የአማራን ህዝብ አጥፋ ተብሎ የተላከው የመከላከያ ሰራዊትና ባንዳው የአማራ ሚሊሻ እንደ ጌሾ ከተወቀጠ በኋላ አንድ አይሱዙ ሙትና ቁስለኛቸውን ተሸክመው ወደ መጡበት ከተማ ፈርጥጠው ለአዛዦቻቸው የመርዶ ነጋሪታቸውን ጎስመዋል።

በድርጊቱ የተበሳጨው የአገዛዙ ወታደር ሙትና ቁስለኛውን ተሸክሞ ሲፈረጥጥ በጎች በመጠበቅ ላይ ያለን አንድ የ70 ዓመት አዛውንት ተኩሰው ገድለውታል። የዉጊያውን ዝርዝር ሁኔታ በስልክ ያደረሱት የሃይለማርያም ማሞ ብርጌድ ዋና አዛዥ ደመላሽ መንግስቴ ጠላት ያለውን ሁሉ ከባድ መሳሪያ ማለትም ዙ-23 ፣ሞርተርና ዲሽቃ ተሸክሞ ፋኖን ለመግጠም ቢሞክርም በሶስቱም የፋኖ ብርጌዶች የወንድማማች ብርቱ ክንድ የአገዛዙ ሰራዊት ተገርፎ መመለሱን አብራርተዋል።

ድል ለአማራ ፋኖ
ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት ክፍል

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Oct, 16:32


https://youtube.com/live/YoJ2ANjzCJc?feature=share

Ethio 251 Media

21 Oct, 16:13


የድል ዜና
/
የአማራ ፋኖ በጎጃም በቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር የስናን አባ ጅሜ እና የንጉስ ተክለሐይማኖት ብርጌድ ባደረጉት የደፈጣ ውጊያ ጠላት እንደ ቅጠል ሲረግፍ ውሏል።

ገና በጡሀቱ ከደብረ ማርቆስ ተነስቶ ወደ ረቡ ገበያ ስንቅ ለማቀበል ሲንቀሳቀስ በነበረው የጠላት ኃይል ላይ የንጉስ ተክለ ሐይማኖት ብርጌድ የፋኖ አባላት በደፈጣ አስደንብረውት ይወጣሉ።
በዚህ የተደናበረው እና በፍራቻ የተዋጠው ፈርጣጭ የአብይ አህመድ ወንበዴ ቡድን እንደገና ሐይሉን አጠናክሮ ከደብረ ማርቆስ ባለ ጎማውን መድፍ፣ዙ23 እና ሞርታር ብሎም ድሽቃውን ጠምዶ ከደብረ ማርቆስ አስፍቶ ወደ ረቡ ገበያ ወጣ።

ረቡ ገበያ ላይ መሽጎ ስንቅ መቀበል አልችል ብሎ ራብ የሚያነጉደውና ህዝቡን እያስገደደ የእለት ጉርሱን የሚደፍነው የጠላት ኃይል ደግሞ ሞርታሩንና ድሽቃውን ጠምዶ ከከተማው ወጥቶ ስንቁን ለመቀበል ጉዞ ጀመረ።

ይህን ሁሉ ግሳንግስ የሚስበው በጡሀቱ አንድ ቲም የንጉስ ተክለ ሐይማኖት ብርጌድ በተተኮሰበት ጥይት ተደናብሮ በልመታ ነው ፍራቻ ነው።
ዳሩ ግን በነበልባሉ ሺ አለቃ ባለው ጊዜ ወንዴ የሚመራው የስናን አባ ጅሜ ብሮጌድ የፋኖ አባላት ሁለቱን ሻለቃ ግራና ቀኝ ደፈጣ አስይዞ ይጠብቀው ኖሯል።
ያልታሰበ ዱብዳ እንራታላይ ጠላት አለ ብሎ ሲጠብቅ የነበረ የአብይ ሽፍታ ቡድን ከረቡ ገበያ በቅሮብ እርቀት ሁለቱ ስንቅ ተቀባይና አቀባይ ሳይገናኙ መንገድ ላይ ያላሰበው ዱብዳ ወረደበት።

የፋኖ ጥይት እንደ ዶፍ ዝናብ ይወርድበት ጀመር።የአብይ ፈርጣጭ ቡድን በየቀኑ ከተወሸቀበት ከተማ ወይም አስፓልት በወጣ ቁጥር ሬሳ እየጫነ መፈርጠጥ ልማዱ ነውና ዛሬም እንደ ትናንቱ ቁጥር ስፍር የሌለው ሬሳና ቁስለኛውን ሬሽን ጭኖበት በመጣው መኪና ጭኖ ተመልሷል።

ይህን ሁሉ ጀብዱ የሚፈፅሙት ሲጥሉ እንጅ ሲዋጉ ለአይን ጥቅሻ የማይታዩት የስናን አባ ጅሜ ብርጌድ የነበልባልና የፋሲካው ሻለቃ የፋኖ አባላት ናቸው።
ከጡሀቱ አራት ሰዓት የጀመረው የደፈጣ ውጊያ ወደ መደበኛ ውጊያ ተሸጋግሮ እስከ እኩለ ቀን ሰባት ሰዓት ድረስ ጠላትን ሲያደባዩት መዋላቸውን የብርጌዱ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ መለሰ ለክፍለ ጦራችን ቃል አቀባይ አርበኛ መ/ር ታደገ (ሸርብ) ገልጧል።
ድል ቁርሱ የሆነው የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ዛሬም በብርጌዶቹ የእለት ተእለት ተጋድሎ ታሪክ በአምዱ እያስመዘገበ ይገኛል።

አማራነት ዘላለማዊነት
አዲስ አብዮት
አዲስ ድል
አዲስ ትውልድ
አዲስ አስተሳሰብ
አዲስ ተስፋ
በወንበዴዎች ወንበር የማይናውዝ አዲስ ትውልድ በክንዳችንና በአንደበታችን እንፈጥራለን።

የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ ፮ኛ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ አርበኛ መ/ር ታደገ ይሁኔ(ሸርብ)


https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

21 Oct, 14:38


"የአማራ ዲያስፖራ ዓለም አቀፍ ገባዔ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል" የአማራ ዓለም አቀፍ ጉባዔ ሰብሳቢ

October 19 እና October 20 በዋሽንግተን ዲሲና ከተለያዩ አገራት በዙም ስብሰባ የተሳተፉበትና የተካሄደውን የአማራ ዲያስፖራ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የጉባዔው ዋና ሰብሳቢ አምባሳደር ብርሃነመስቀል ነጋ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል።

በዚህ ጉባኤ ላይ በዓለም ያሉ ከሰላሳ በላይ የአማራ ማህበራት፣ በአሜሪካ የሚገኙ ከተለያዬ ስቴት የመጡ በርካታ ቁጥር ያላቸው አማራዎች፣ ምሁራን፣ የሚዲያ አባላት፣ በመጭው የአሜሪካ ምርጫ የሚወዳደሩ ተመራጭ አካላት ተሳትፈው ውሳኔና የትግል አቅጣጫ ማስቀመጣቸውን አምባሳደር ብርሃነመስቀል ነጋ ለጣቢያችን ገልጸዋል።

አምባሳደር ብርሃነመስቀል ነጋ፤ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት የምንሰራቸውን ዝርዝር ስራዎች በመግለጫ ይፋ እናደርጋለን ብለዋል።

ዝርዝር መረጃዎች አሉት "በ251 ዛሬ" ዝግጅታችን ይጠብቁን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 18:22


ትዊተር (X) ላይ የተጀመረውን ዘመቻ ተቀላቀሉ።

https://x.com/251media?s=21

Ethio 251 Media

17 Oct, 14:28


ሰበር ዜና!

122ኛ ሬጅመንት ሙሉ ለሙሉ ፈርሷል!

በወሎ ቤተ-አማራ ሰሞኑን በተደረገው ተጋድሎ 101ኛ ኮር 122ኛ ሬጅመንት ሙሉ ለሙሉ ማፍረሱን የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ ገለጸ።

የአማራ ፋኖ በወሎ ከሰሞኑ ባደረገነው ተከታታይ ውጊያ ከፍተኛ ድል ተቀደጅተናል ሲል የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ ዋርካው ምሬ ወዳጆ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

በዚህ ውጊያ ከባድ መሳሪያዎችን ጨምሮ የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ፋኖዎቻችን ብቻ ሳይሆን ሕዝባችን አስታጥቀናል፤ የሰሜን ምስራቅ ዕዝ 101ኛ ኮር 122ኛ ሬጅመንት የሰው ኃይል አስተደዳር አብዳላሒ ናስር፣ የአንድ ሻለቃ ዋና አዛዥና ዘመቻ መምሪያ ኃላፊን ጨምሮ የ122ኛ ሬጅመንት ከፍተኛ አመራሮች ተደምስሰዋል፣ 122ኛ ሬጅመንት ገሚሱን ስንደመስሰው፣ ቀሪውን ማርከነዋል፤ ከምርኮና ከድምሰሳ የተረፈውን የመልቀም ስራ እየሰራን ነው ሲል ዋርካው ምሬ ወዳጆ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

አገዛዙ፤ በአማራ ፋኖ በወሎ ከዋግኽምራ እስከ አማራ ሳይንት ቀጠና ከፍተኛ ኪሳራ የደረሰበትን ምት መቋቋም ሲያቅተው በድርጅታችን ስም ሀሰተኛ መረጃውን እየፈበረከ ሲያሰራጭ ተመልክተናል፤ በውሸት ዜና የሚገኝ ድል እንደሌለ መግለጽ እንፈልጋለን ሲል ዋርካው ምሬ ወዳጆ ገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪ አገዛዙ ባልታጠቀው ሕዝባችን ላይ ሁሉን አቀፍ ጥቃት ከፍቷል፤ ይህንን ሁሉ አቀፍ ጥቃትም በመደራጀት ሊመክት እንደሚገባ ገልጿል።

የአማራ ፋኖ በወሎ ዋና አዛዥ ጋር ያደረግነው ቃለምልልስ በኢትዮ 251 ሚዲያ "251 ዛሬ" ይጠብቁን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 11:04


ሰበር ዜና!

በአርበኛ ባዬ ቀናው የሚመራው የአማራ ፋኖ በጎንደር ደብረ ታቦር ከተማ ዘልቆ በመግባት ልዩ ኦፕሬሽን ፈፀመ።

የአማራ ፋኖ በጎንደር በፋኖ ተመስገን ውባንተ አባተ የሚመራው ሜጀር ጀነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክፍለጦር በዛሬው ዕለት ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ከቀኑ 5 ሰዓት ጀምሮ ለ25 ደቂቃ በፈጀው ልዩ ኦፕሬሽን ደብረተ ታቦር ከተማ ልዩ ስሙ ፀጉር ኪዳነምህረት ሰፈር ላይ የአገዛዙን ወታደር ድባቅ እንደተመታ የአማራ ፋኖ በጎንደር ምክትል የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ፋኖ ሀቃለው ፀጋ አለባቸው ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

25 ደቂቃ በወሰደው ቀዶ ጥገና ወይም ልዩ ኦፕሬሽን የአገዛዙን ወንበር ጠባቂ ሰራዊት በማፍረስ 4 ሲደመሰሱ፣ 3 መማረክ መቻሉን ፋኖ ሀቃለው ፀጋ አለባቸው አክሎ ለጣቢያችን ገልጿል።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 10:15


በጎጃም ቀጠና ባሉ የግንባር ተጋድሎዎችን እንዲሁም አገዛዙ ያደረሳቸው ውድመቶችንና ጥፋቶች በተተመለከተ:-

የአማራ ፋኖ በጎጃም ፋኖ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ፋኖ ዮሃንስ አለማየሁ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 09:44


ጥብቅ - መረጃ

ባለፈው ሳምንት የወጣውን የደህንነት ተቋማት መረጃ ተከትሎ በደህንነት መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ መደናገጥ ተፈጥሯል።

የውስጥ አርበኞች ለኢትዮ 251 ያደረሱትን መረጃ ጋዜጠኛ ሙሉጌታ አንበርብር ያቀርበዋል።

ተከታተሉት...

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 09:30


የተሀድሶ ፕሮግራም በማካሄድ ሠራዊቱን ለተሻለ ግዳጅ ማዘጋጀቱን የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ  አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ባዘጋጀው የተሃድሶ ፕሮግራም ጉልህ አስተዋፅኦ ለነበራቸው ብርጌዶች የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ አፄ ዳዊት ክፍለ ጦር ለኢትዮ 251 ሚዲያ ያደረሰውን መረጃ ጋዜጠኛ እንዳልካቸው አባቡ አቅርቦታል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 09:11


በሸዋ ቀጠና አገዛዙ የሚደርስበትን ምት እና ሽንፈት መቋቋም ባለመቻሉ ንፁሃንን ኢላማ ያደረገ ጥፋት እያደረሰ መሆኑ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ምክትል የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ ንጋቱ ይታፈሩ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 08:52


አገዛዙ በድሮንና በመድፍ ጥቃት ንብረት እያወደመና ንፁሃንን እየገደለ መሆኑ ተገለፀ።

የአማራ ፋኖ በወሎ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ ፋኖ አበበ ፈንታው በዝርዝር ጉዳዮች ላይ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት ....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 08:30


አገዛዙ በዳንግላ የድሮን ጥቃት ፈፀመ!

በዛሬው ዕለት ጥቅምት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከጧቱ ሶስት ሰዓት ላይ በዳንግላ ወረዳ ልዩ ስሙ አፈሳ የሚባል ቦታ ላይ በተፈፀመ የድሮን ጥቃት 8 ንጹሃን ሲገደሉ፣ 7 ንጹሃን ቆስለዋል፤ በተጨማሪም 3 ከብትና 4 በግ መገደላቸውን የአይን እማኞች ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጸዋል።

የአብይ አህመድ አገዛዝ መጠነ ሰፊ የሆነ የአየር ጥቃት በንጹሃን ላይ የከፈተ ሲሆን በዚህ ሳምንት ከወትሮው በተለዬ ተባብሶ እንደቀጠ ጣቢያችን ለመገንዘብ ችላለች!

በዝርዝር መረጃ እንመለሳለን።

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

17 Oct, 08:09


ከጋሳይ ወደ ስማዳ ሲንቀሳቀስ በነበረ የጠላት ሃይል ላይ እርምጃ ተወስዶበታል።

የአገዛዙን የጥፋት እቅድና የድል ውጤቶች በተመለከተ የአማራ ፋኖ በጎንደር የዘመቻ መምሪያ ሃላፊ እና የገብርዬ ክፍለ ጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ከፍያለው ደሴ ከኢትዮ 251 ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ተከታተሉት....

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

16 Oct, 18:49


የX #campaign ተቀላቀሉ!

👇👇👇👇👇👇👇
https://x.com/251media?s=21

Ethio 251 Media

16 Oct, 17:53


Live stream finished (2 hours)

Ethio 251 Media

16 Oct, 16:24


በደቡብ ወሎ ዞን የተንታ ወረዳ የሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊ መገደሉ ተሰማ!

የተንታ ወረዳ የሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊው አቶ ስለሺ ተስፋዬ ዛሬ ጥቅምት 06/2017 ዓ/ም ማርፈጃውን በአጅባር ከተማ ውስጥ መገደሉን ነው መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው።

በሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊው ላይ እርምጃውን የወሰዱት በአማራ ፋኖ ወሎ ዕዝ የልጅ እያሱ ኮር ፋኖዎች መሆናቸውንም ለጣቢያችን የደረሰው መረጃ ያመለክታል ሲል መረብ ሚድያ ገልጿል።

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

16 Oct, 15:30


Live stream started

Ethio 251 Media

16 Oct, 15:27


ወሎ ቤተ-አምሃራ

አገዛዙ ንፁሃንን እየጨፈጨፈ ንብረትም እታወደመ ነው::

የኦነግ ብልፅግና አገዛዝ በዙፋን ጠባቂ ሰራዊቱ መቀመጫዉን ቆቦ ከተማ ሆርማት ያደረገ መድፍ ወደ ተኩለሽና አካባቢው በማስወንጨፍ በዋ ሚካኤል ንፁሃን ላይ እና ከብቶች ላይ ከባድ ጉዳት አድርሶዋል::

በዘፈቀደ እየተወነጨፈ ያለው መድፍ በዋ ሚካኤል የሚባል የራያ ቆቦ ቀበሌ ላይ 6 (ስድስት) ህፃናት ያቆሰለ ሲሆን 18 (አስራ ስምንት) ከብቶችን ገድሎዋል::

ከንፁሃን ሞት በተጨማሪ አገዛዙ ተቁዋማቶችን እያወደመ ያለ ሲሆን ሰሞኑን ራያ ቆቦ አዋስ ጤና ጣቢያን በወርቄው ባንዳ በካሪስ ጎቤ እየተመራ ሙሉ ለሙሉ አውድመው መድሃኒትና አጠቃላይ ንብረቱን ጭነው በመዉሰድ ተስፋ የቆረጡ የአገዛዙ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆን ለግል ጥቅማቸው እንዳዋሉት አረጋግጠናል::

እየወደሙ ካሉ ጤና ጣቢያዎችና ትምህርት ቤቶች በተጨማሪ የማህበረሰቡን ሱቆች የሚዘርፉትን ዘርፈው የተረፈዉን በማውደም ህዝባችንን የበቀል ዱላቸዉን እያሳረፉበት ይገኛሉ::

በመሆኑም ሁለንተናዊ ጥቃታችንም ይሁን ሞታችን የሚቆመውና ዘላቂ መፍትሔ የሚመጣው በጀመርነው የህልዉና ተጋድሎ ነውና የአማራ ህዝብ እንደ ህዝብ በመቆም ተጋድሎዉን እስከ ድል አጠናክሮ ማስቀጠል ይኖርበታል::

ድል ለፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም.

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

16 Oct, 15:24


"አብይ አህመድ ሆይ ድርድር ሲያምርህ ይቀራል::" የአማራ ፋኖ በወሎ

ዛሬ በድል ዋዜማ ላይ ሆነን ሳይሆን ያኔ ትግሉን "ሀ" ብለን ስንጀምር ብቸኛ አማራጫችን "ማሸነፍ" ብቻ መሆኑን አምነን ተማምለን ነው የወጣነው:: ይህንን ስንልና ድርድርን ስንጠየፍ በምክንያት እንጂ እንዲሁ ሾላ በድፍኑ አይደለም:: ለትግል የወጣነው በሃገራችን ባይተዋር ሆነን ፍፁም ሰላም አጠተን በአጠቃላይ ህልዉናችን አደጋ ላይ ስለወደቀ ነው::

የህልዉና አደጋው ህገ-መንግስት ተቀርፆለት መዋቅራዊና መንግስት መር በመሆኑ ስርአቱን ከመደምሰስና ከመገርሰስ ዉጭ ሌላ አማራጭ እንደሌለን ሞተን የፈተነው ሃቅ መሆኑን በመገንዘብ ነው::

ስለሆነም በአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀመ ያለው የአብይ አህመዱ የኦነግ ብልፅግና መንግስት ለህልዉናው እየታገለ ባለው የአማራ ፋኖ ትግል ጣእረ ሞት ላይ መሆኑንና መሸነፉን ስለተረዳ ሴራና ሃሰተኛ ፕሮፓጋንዳ ላይ ተጠምዶ ይገኛል::

በመሆኑም መላው የአማራ ፋኖና ህዝባችን ይህንን የጠላት የጣእረ ሞትና የሽንፈት መንገድ በመረዳትና በመገንዘብ ሙሉ ትኩረቱን ትግሉ ላይ እንዲያደርግ ስንል መልክታችንን እናስተላልፋለን::

ድል ለፋኖ
ድል ለአማራ ህዝብ
የአማራ ፋኖ በወሎ
ጥቅምት 6/2017 ዓ.ም

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

16 Oct, 13:30


ሰበር ዜና!

“አገዛዙ እንደ ሕዝብ ሊያጠፋን እየተንቀሳቀሰ ነው፣ እኛም እንደ ሕዝብ በመነሳት የጠላትን ኃይል ማጥፋት አለብን” አርበኛ ከፍያለው ደሴ

የአብይ አህመድ አገዛዝ የአማራን ሕዝብ አንገት ለማስደፋት ሁሉን አቀፍ ጥቃት ከፍቷል፣ እኛም ይሄን ጥቃት እየመከትን እንገኛለን፣ በትላንትው እለት ከክምር ድንጋይ የተነሳውን የጠላት ኃይል የአማራ ፋኖ በጎንደር ገብርዬ ክፍለጦር ጨጨሆ ብርጌድ ስማዳ መገንጠያ ላይ ደፈጣ በመጣል ድባቅ እንደመቱት የማራ ፋኖ በጎንደር የዘመቻ መምሪያ ኃላፊና የገብርዬ ክፍለጦር ዋና አዛዥ አርበኛ ከፍያለው ደሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ ገልጿል።

የፋኖዎችን ምት መቋቋም ያቃተው የአብይ አህመድ ወንበር ጠባቂ ወታደር በንጹሀን ላይ ከፍተኛ ግፍ እየፈፀመ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ደብረታቦር ዙሪያ ለአረም የወጡ አራት ንጹሃንን በሰልፍ በማሰለፍ በዲሽቃ መረሸኑን፣ በተጨማሪም ለሰብል አረም የተቀመጡ ንጹሃንን ደፈጣ ይዛችሁ ነው በሚል በሰብል ማሳቸው ላይ ከአስር በላይ ንጹሃን መጨፍጨፉን አርበኛ ከፍያለው ደሴ ለኢትዮ 251 ሚዲያ አክሎ ገልጿል።

አርበኛ ከፍያለው ደሴ “ጠላት እንደ ሕዝብ ሊያጠፋን ነው የመጣው፣ ሕዝቡን ሳይሆን መሬቱን ብቻ እንደሚፈልጉት በተጨባጭ እያሳዬ ነው፣ በመሆኑም ማጭድ ያየዙ ገበሬዎችን ጦር መሳሪያ ነው የያዛችሁት በሚል የሚንቀሳቀሰውን የጠላት ኃይል ሆ ብሎ በመነሳት መደምሰስ ያስፈልጋል።” ብሏል!

ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን በ251 ዛሬ ዝግጅታችን ይጠብቁን!

ኢትዮ 251 ሚዲያ
የነጻነት አንደበት!

https://t.me/ethio251media

Ethio 251 Media

16 Oct, 12:46


📌ሰዓት እየደረሰ ነው፣ አካውንት ከፈታችሁ ወይ⁉️

በተለይ በዛሬው እለት ለመጀምር የታሰበው የቲውተር ዘመቻ ያለውን ተፅኖ ስለሚያውቅ አግዛዙ ገመናየ ሊጋለጥብኝ ነው በሚል ከፍተኛ ፍረሃት ውስጥ የገባ ሲሆን ይህንኑም ዘመቻ በዋናነት ይመሩታል ተብለው የታሰቡ የአማራ አክቲቪስቶችን (በላይ ማናዬ፣ ሙሉጌታ አንበርብር፣ አሳዬ ደርቤ እና መዓዛ መሀመድ እና ሌሎችንም) እና የአማራ ድምፅ ሚዲያዎችን የማህበራዊ ገፅ ለማዘጋት የአገዛዙን የሚዲያ ሰራዊት ተጠቅሞ ሪፖርተ በማደረግ ለማዘጋት እንቅሰቃሴ ተጀምሯል፡፡ የኢሜልና የማህበራዊ ሚዲያ አካውንቶቻችሁንም ሀክ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ከዚህ ጋር በተየያዘ የደህነንት ተቋማቱ ኬንያ ከሚገኘው ከሜታ ካምፓኒ ጋርም ተደጋጋሚ ስበሰባ በማድረግ በዚሁ ጉዳይ ላይ እየተነጋገሩ ይገኛሉ፡ በዚሁ ጉዳይ በኬንያ የኢትዮጵያ ኢንባሲ ጭምር ጉዳዩን ይዞ እየሰራበትና የሜታ ተወካዮችን ሎቢ ለማድረግ እየሞከረ ነው፡፡

የታሰበውን የቲውተር ዘመቻ ለማስተባበል እና ካውንተር ለማድረግ የአገዛዙ የሚዲያ ሰራዊት ትዊተር ላይ የሚሰጣቸውን የማስተባበያ ኮንተንት በተመሳሳይ ሰአት ትዊት እንዲያደርጉ፣ ኮሜንት እና ሪፖርት እንዲያደርጉ አቅጣጫ ተሰቷል፡፡

ከሚዲያ ሰራዊቱ በተጨማሪ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ተቋም በኩል ከውጭ የገዟቸውን ቦቶች ሳይቀር ተጠቅመው እንዲሰሩና እና በምንም አይነት መልኩ የትዊተር እና የሚዲያ ብልጫ እንዳይወሰድባቸው ከዚህ ቀደም መረጃው ላይ በስም የተጠቀሱት አመራሮች ትኩርት ሰጠው እንዲሰሩ እቅጣጫ ተሰጥቷቸዋል፡፡


📌እኛም ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ ሁለት ቀን የሚቆይ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ሁሉን አቀፍ ጥቃት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳወቅ X ላይ ዘመቻ ይኖረናል። ሁሉም ይዘጋጅ።

የX አካውንት የሌላችሁ ክፈቱ!
👇👇👇👇👇👇👇
https://x.com/251media?s=21