ሁለት ልጆችን ከቤተሰቦቻቸዉ እዉቅና ዉጪ ሰርቆ በመዉሰድ በጉልበት ስራ ላይ ሲያሰማራ የነበረዉ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጂዳ ወረዳ ዉስጥ ሲሆን ገዜ ታምሩ በተባለ ግለሰብ አማካይነት ነዉ ። ህፃናቱን በተለያየ ጊዜ እና ቀን ከቤተሰቦቻቸው እዉቅና ዉጪ ሰርቆ በመዉሰዱ በእስራት መቀጣቱን የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት ገልጿል ።
የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት የተለያዩ ወንጀሎችና የነፍስ ግድያ ምርመራ ክፍል ኃላፊ አቃቤ ህግ አብዮት አስፋዉ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ግለሰቡ ሀምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በጂዳ ወረዳ ስርጤ ከተማ ዉስጥ ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ ከትምህርት ቤት በመመለስ ላይ የነበረዉን የ14 አመት ልጅ በወር 25ሺህ ብር ክፍያ ታገኛለህ አዲስአበባ ስራ ላስቀጥርህ በማለት አታሎ በመዉሰድ ለጉልበት ስራ እንዳሰማራዉ ገልጸዋል ።
ይህዉ ተከሳሽ ከ3 ቀናት በኋላ ከአዲስአበባ በመመለስ የ13 አመት ልጅን በወር 20ሺህ ብር የሚያገኝበት ስራ እንዳገኘለት በመንገር ከቤተሰቦቹ ሰርቆ በመዉሰድ ወደ አዲስአበባ በመጓዝ ላይ ሳሉ ሙቀጥሬ ከተማ ኬላ ላይ በቁጥጥር ስር ዉሏል ። ተከሳሹ ህፃናቱን አታሎ በመዉሰድ ለጉልበት ስራና ብዝበዛ እንዲገላጡ አድርጓ። ፖሊስ ተከሳሹን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ የምርመራ መዝገቡን በበቂ ማስረጃ በማደራጀት ለአቃቤ ህግ ልኳል ።
አቃቤ ህግም ህገወጥ የሰዎች ዝዉዉርን ለመቆጣጠር የወጣዉን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እና በወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ አንቀጽ 3 መሠረት ክስ መስርቷል ። ክሱን ሲከታተል የቆየዉ የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተካሳሹን ጥፋተኛ በማለት በ10 ዓመት እስራትና በ10 ሺህ ብር መቀጮ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን አቶ አብዮት አስፋዉ ገልጸዋል ።
በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56
👉 https://www.facebook.com/mik0Man
Canais Semelhantes



ዳጉ-ጆርናል: የመረጃ ምንጭና የጋዜጠኞች ስነምግባር
ዳጉ-ጆርናል በአማርኛ እና በሀላፊ መረጃ የገጽ አቀማመጥ ጋዜጠኞች የሚቀጥሉትን ቦታ ነው። ይህ ቦታ የአማርኛ ቋንቋ በሚገጽበት ዓለም ውስጥ 'ሙዚቃ ወቅታዊ' በሚባለው ዓይነት ይገኛል። ዳጉ-ጆርናል በአውዛይ ወንበር ወይም በሌሎች ቦታዎች የሚሰጡው የመረጃ ዓይነት የአማርኛ መረጃ ምንጭ እንደሆነ ጥንቃቄ ነው። ዳጉ-ጆርናል የሙያው ስነምግባር የተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ይህ እንደ ዝንባሌ ወርቅ ይንቀትቃል።
ዳጉ-ጆርናል ምን ነው?
ዳጉ-ጆርናል በአማርኛ የተመለከተ የመረጃ ምንጭ እና የጋዜጠኞች ስነምግባር ነው። ይህ የተቋቋሙ መረጃዎች መነሻ እንደሆነ በዋነኛ ምንጭ ተጠቃሚ ይሆናል።
ምንም እንኳን ዳጉ-ጆርናል በገንዘብ ላይ የተመለከተ ነገር እንዳለው ይታወቃል። ነገር ግን ዳጉ-ጆርናል ነው እንደሚባለው መረጃ ትርጉም ይታወቃል።
ዳጉ-ጆርናል እንዴት ይሰራል?
ዳጉ-ጆርናል በድምፅ እና ባህላዊ ቁልፍ መረጃ ተሞልቶ ይሰራል። ይህን ዳጉ-ጆርናል የሚያርግ ጋዜጠኞች ግን ሙዚቃ ወቅታዊ ወይም በሌላ ቦታ ዝርዝር ሙዚቃን ይሰጣሉ።
በዳጉ-ጆርናል ውስጥ በተለይም ከእጅ ጋር የተያያዘ መረጃዎች ይኖራሉ። ነበር የተወጀ ዳጉ-ጆርናል የፌስቡክ ድር ጣቢያ እና ነገር ሌላ የተመለከተ ማህበረሰብ እንዲሆን ይሠናበታል።
ዳጉ-ጆርናል የሚያቀርቡት የመረጃ ባለው ተፈጻሚ ነገር የማለት ምን ነው?
ዳጉ-ጆርናል ቀረባሪዎቹ የጋዜጠኞች ዕይታ ሚድያ የሚያካሂዱ ምንጭ እና ተግባርዎቹ ያንጻል። ይህ በመረጃ ማንነት እንደሚሰጠው የማይወርድ ምን ይወጣል።
ዳጉ-ጆርናል ማንነት ይወጣል የመረጃ ምንጭ የመነሻ እንደሆነ ነው። የጋዜጠኞች በምንጭ አቀማጥታ ይሰጣል።
Canal ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal no Telegram
ዳጉ-ጆርናል ብቻ የሚወስድ ታሪክ በቅርብ ምኞት የታሪከ፣ ብሄር ጊዜ። እንደተግባር በገሞሩበት ሁኔታ መልካም ተዓማኒ ለማስታበቢዎት እና ለሙያው ሀበሻችን ብቻ ያግኙን። ትርጉም፡ ዳጉ-ጆርናል ብቻ የሚወስድ ታሪክ በቅርብ ምኞት የታሪከ፣ ብሄር ጊዜ። እንደተግባር በገሞሩበት ሁኔታ መልካም ተዓማኒ ለማስታበቢዎት እና ለሙያው ሀበሻችን ብቻ ያግኙን።