Canal ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal @zena24now no Telegram

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal
The best fiction is far more true than any journalism

📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ

👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56



👉 https://www.facebook.com/mik0Man
43,747 Inscritos
26,279 Fotos
228 Vídeos
Última Atualização 23.02.2025 02:33

Canais Semelhantes

Borkena
7,257 Inscritos

ዳጉ-ጆርናል: የመረጃ ምንጭና የጋዜጠኞች ስነምግባር

ዳጉ-ጆርናል በአማርኛ እና በሀላፊ መረጃ የገጽ አቀማመጥ ጋዜጠኞች የሚቀጥሉትን ቦታ ነው። ይህ ቦታ የአማርኛ ቋንቋ በሚገጽበት ዓለም ውስጥ 'ሙዚቃ ወቅታዊ' በሚባለው ዓይነት ይገኛል። ዳጉ-ጆርናል በአውዛይ ወንበር ወይም በሌሎች ቦታዎች የሚሰጡው የመረጃ ዓይነት የአማርኛ መረጃ ምንጭ እንደሆነ ጥንቃቄ ነው። ዳጉ-ጆርናል የሙያው ስነምግባር የተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ይህ እንደ ዝንባሌ ወርቅ ይንቀትቃል።

ዳጉ-ጆርናል ምን ነው?

ዳጉ-ጆርናል በአማርኛ የተመለከተ የመረጃ ምንጭ እና የጋዜጠኞች ስነምግባር ነው። ይህ የተቋቋሙ መረጃዎች መነሻ እንደሆነ በዋነኛ ምንጭ ተጠቃሚ ይሆናል።

ምንም እንኳን ዳጉ-ጆርናል በገንዘብ ላይ የተመለከተ ነገር እንዳለው ይታወቃል። ነገር ግን ዳጉ-ጆርናል ነው እንደሚባለው መረጃ ትርጉም ይታወቃል።

ዳጉ-ጆርናል እንዴት ይሰራል?

ዳጉ-ጆርናል በድምፅ እና ባህላዊ ቁልፍ መረጃ ተሞልቶ ይሰራል። ይህን ዳጉ-ጆርናል የሚያርግ ጋዜጠኞች ግን ሙዚቃ ወቅታዊ ወይም በሌላ ቦታ ዝርዝር ሙዚቃን ይሰጣሉ።

በዳጉ-ጆርናል ውስጥ በተለይም ከእጅ ጋር የተያያዘ መረጃዎች ይኖራሉ። ነበር የተወጀ ዳጉ-ጆርናል የፌስቡክ ድር ጣቢያ እና ነገር ሌላ የተመለከተ ማህበረሰብ እንዲሆን ይሠናበታል።

ዳጉ-ጆርናል የሚያቀርቡት የመረጃ ባለው ተፈጻሚ ነገር የማለት ምን ነው?

ዳጉ-ጆርናል ቀረባሪዎቹ የጋዜጠኞች ዕይታ ሚድያ የሚያካሂዱ ምንጭ እና ተግባርዎቹ ያንጻል። ይህ በመረጃ ማንነት እንደሚሰጠው የማይወርድ ምን ይወጣል።

ዳጉ-ጆርናል ማንነት ይወጣል የመረጃ ምንጭ የመነሻ እንደሆነ ነው። የጋዜጠኞች በምንጭ አቀማጥታ ይሰጣል።

Canal ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal no Telegram

ዳጉ-ጆርናል ብቻ የሚወስድ ታሪክ በቅርብ ምኞት የታሪከ፣ ብሄር ጊዜ። እንደተግባር በገሞሩበት ሁኔታ መልካም ተዓማኒ ለማስታበቢዎት እና ለሙያው ሀበሻችን ብቻ ያግኙን። ትርጉም፡ ዳጉ-ጆርናል ብቻ የሚወስድ ታሪክ በቅርብ ምኞት የታሪከ፣ ብሄር ጊዜ። እንደተግባር በገሞሩበት ሁኔታ መልካም ተዓማኒ ለማስታበቢዎት እና ለሙያው ሀበሻችን ብቻ ያግኙን።

Últimas Postagens de ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal

Post image

ሁለት ልጆችን ከቤተሰቦቻቸዉ እዉቅና ዉጪ ሰርቆ በመዉሰድ በጉልበት ስራ ላይ ሲያሰማራ የነበረዉ ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመዉ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጂዳ ወረዳ ዉስጥ ሲሆን ገዜ ታምሩ በተባለ ግለሰብ አማካይነት ነዉ ። ህፃናቱን በተለያየ ጊዜ እና ቀን ከቤተሰቦቻቸው እዉቅና ዉጪ ሰርቆ በመዉሰዱ በእስራት መቀጣቱን የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት ገልጿል ።

የሰሜን ሸዋ ዞን አቃቤ ህግ ፅህፈት ቤት የተለያዩ ወንጀሎችና የነፍስ ግድያ ምርመራ ክፍል ኃላፊ አቃቤ ህግ አብዮት አስፋዉ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት ግለሰቡ ሀምሌ 25 ቀን 2016 ዓ.ም በጂዳ ወረዳ ስርጤ ከተማ ዉስጥ ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ ከትምህርት ቤት በመመለስ ላይ የነበረዉን የ14 አመት ልጅ በወር 25ሺህ ብር ክፍያ ታገኛለህ አዲስአበባ ስራ ላስቀጥርህ በማለት አታሎ በመዉሰድ ለጉልበት ስራ እንዳሰማራዉ ገልጸዋል ።

ይህዉ ተከሳሽ ከ3 ቀናት በኋላ ከአዲስአበባ በመመለስ የ13 አመት ልጅን በወር 20ሺህ ብር የሚያገኝበት ስራ እንዳገኘለት በመንገር ከቤተሰቦቹ ሰርቆ በመዉሰድ ወደ አዲስአበባ በመጓዝ ላይ ሳሉ ሙቀጥሬ ከተማ ኬላ ላይ በቁጥጥር ስር ዉሏል ። ተከሳሹ ህፃናቱን አታሎ በመዉሰድ ለጉልበት ስራና ብዝበዛ እንዲገላጡ አድርጓ። ፖሊስ ተከሳሹን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ የምርመራ መዝገቡን በበቂ ማስረጃ በማደራጀት ለአቃቤ ህግ ልኳል ።

አቃቤ ህግም ህገወጥ የሰዎች ዝዉዉርን ለመቆጣጠር የወጣዉን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እና በወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ አንቀጽ 3 መሠረት ክስ መስርቷል ። ክሱን ሲከታተል የቆየዉ የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተካሳሹን ጥፋተኛ በማለት በ10 ዓመት እስራትና በ10 ሺህ ብር መቀጮ እንዲቀጣ የተወሰነበት መሆኑን አቶ አብዮት አስፋዉ ገልጸዋል ።

በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል

22 Feb, 09:38
5,533
Post image

በ2017 ዓመት በአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ካጋጠሙት 144 የእሳት አደጋዎች ውስጥ 57ቱ  የቤት ቃጠሎ ነው

በአዲስ አበባ የሚደርሱት አብዛኛው ድንገተኛ አደጋዎች የሚከሰቱት ከጥንቃቄ ጉድለት መሆኑንም የአዲስ አበባ ከተማ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

በየዓመቱ በአዲስ አበባ እና ዙሪያዋ በርካታ ከፍተኛ እና መለስተኛ አደጋዎች የሚከሰቱ ሲሆን ባለፈው ስድስት ወራት ብቻ 244 አደጋዎች ያጋጠሙ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ 144 የሚሆኑት የእሳት አደጋ ፤ ቀሪው 100 አደጋ ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች መሆናቸው ተነግሯል።

ካጋጠሙት 144 የእሳት አደጋዎች ውስጥ 57  የቤት ቃጠሎ በመሆን ቅድሚያ የሚይዝ ሲሆን ይህም ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ 737 የሚሆኑት አደጋዎች በመኖሪያ ቤት ያጋጠሙ ናቸው።

የንግድ ሱቆች በሁለተኛ እና ፋብሪካዎች እና ሌሎች ተቋማት ተከታዩን ደረጃ ይይዛሉ።በተመሳሳይም በበጀት ዓመቱ ካጋጠሙት 100 ድንገተኛ አደጋዎች ውስጥ የመጀመሪያ ደረጃ  የሚይዘው የጎርፍ አደጋ መሆኑን ተገልፃል።

በከተማዋ በተደጋጋሚ ስለሚከሰቱ የእሳት እና ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች አስቀድሞ በመከላከል እና ሲከሰትም የከፍ ጉዳት ሳያደርሱ መከላከል በሚቻልበት መንገዶች ዙሪያ ኮሚሽኑ ዛሬ ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር  ውይይት አድርጓል።

በውይይቱ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ኮማንደር አህመድ መሃመድ ለብስራት ሬድዮ እና ቴለቪዥን እንደተናገሩት እነዚህ አደጋዎች መንስኤቸው ሲጣራ አብዛኛው ከጥንቃቄ ጉድለት የሚከሰቱ ናቸው ብለዋል።

ይህንን ከጥንቃቄ ጉድለት የሚከሰቱ ድንገተኛ አደጋዎችን ለመከላከል ሁሉም በጋራ መስራት አለበት የተባለ ሲሆን ለህብረተሰቡም የግንዛቤ ማስጨበጫ መስራት እንደሚጠበቅ ኮሚሽነር ኮማንደር አህመድ ማሀመድ ጨምረው ተናግረዋል።

በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል

22 Feb, 08:27
6,083
Post image

ቅዳሜን ከእኛ ጋር" ፕሮግራም በተወዳጁ ብስራት ኤፍ.ኤም 101.1 ዛሬ ይመለሳል፤ ስንመለስ...

[ ] በልዩ ፕሮግራም ቅዳሜን ከእኛ ጋር ዛሬ የሬዲዮ ሞገዳችሁን 101.1 ላይ ካደረጋችሁ አብረን እንቆያለን። 

[ ]  ለትወና ከተፈጠሩ ሰዎች ውስጥ አንዷ ናት፤ ከተሰጣት ገፀ ባህሪ በላይ መሆን የምትችል እና በኮሜዲ ትወና ውስጥ ከጥቂት ሴት ተዋንያኖች መካከል አንዷ የነበረችውን አርቲስት ሰብለ ተፈራን እንዘክራታለን።

[ ] ሀማስ በማያስተዳድረው የፍልስጥኤም ግዛት ዌስት ባንክ የእስራኤል ጥቃት ለምን ቀጠለ?

[ ] የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የ26ኛ ሳምንት የመክፈቻ ጨዋታ እሮብ ሲመለስ ቪላ ፓርክ ላይ ሉቨርፑል በሽርፍራፊ ሰከንዶች ነጥብ ጥሏል። ዛሬ በምሳ ሰዓት ጨዋታ ኤቨርተን ከማንችስተር ዩናይትድ ይገናኛሉ። ምሽት ላይ ኤምሬትስ ላይ ደጋግመው በማሸነፍ የሚታወቁት ዴቩድ ሞይስ ዘንድሮ ደካም የሆነውን ዌስትሃም ይዘው አርሰናልን ይገጥማለ። የሳምንቱ ሌላኛው ተጠባቂ ጨዋታ ቪላ ፓርክ ላይ አስቶንቪላ ከቼልሲ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል። ነገ በእለተ እሁው ኢትሃድ ላይ ማንችስተር ሲቲ ከሊቨርፑል የሚያደርጉት የሳምንትቱ ትልቁ ጨዋታ ይሆናል። ግምታችሁን ላኩልን

[ ] የቅዳሜ ወሬዎችን እያነሳሳን እንቆያለን ምርጥ ምርጥ ሙዚቃ ትጋበዛላችሁ፤ ተረክም አለ ፣ ስፖርታዊ ጥንቅር ከወቅታዊ መረጃዎች ጋር ተዘጋጅቷል።

ስፖንሰሮቻችን ፦
👉 ዘመን ባንክ
👉 ቨርጂኒያ ፋርማሲውቲካልስ
👉 ጣዕም ዳቦና ኬክ ቤት-ሻወርማን ይቅመሱ
👉 ማር ህይወት ሆስፒታል
👉 ጃፋር የመፅሃፍት መደብር
👉ዲያፕላንትስ - ፍቱን የባህል ህክምና
👉 አውት ዲተርጀንት -የፅዳት መላ

ሁሌም ቅዳሜያችሁን ከ 5 እስከ 7 በተወዳጁ ጣቢያ ብስራት ኤፍ.ኤም 101.1 ላይ እንጠብቃችኃለን።

#ቅዳሜን ከእኛ ጋር
ለአዳዲስ እና ወቅታዊ መረጃዎች ቴሌግራም ቻናላችንን #ዳጉ_ጆርናል ይቀላቀሉ
ሊንክ :- @zena24now

22 Feb, 06:42
6,032
Post image

አዋጭ ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ ብር ለሜቄዶንያ ለገሰ

አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ህብረት ስራ ማህበር ለሜቄዶንያ 2,500,000 (ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ )ብር ለግሷል።

አንድ ሚሊየን ብር በቁጠባና ብድር አንድ ሚሊየን በፋውንዴሽኑ አምስት መቶ ሺህ ብር ከሰራተኞቹና ከአባላት በአጠቃላይ ሁለት ሚሊየን አምስት መቶ ሺህ ለመቅዶኒያ አስገብቷል።

በቀጣይም በየአመቱ አንድ ሚሊየን ብር ለመስጠት ቃል ገብተዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

22 Feb, 06:25
5,580