❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️ @terbinos Channel on Telegram

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

@terbinos


« ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወይሰመይ ስሙ አማኑኤል ዘበ ትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ »
••••
« ድንግል ትፀንሳለች ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ሰሙንም አማኑኤል ትለዋለች ትርጉሙም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ
••••
ቻናላችንን ይቀላቀሉ ዘንድ ግብዣችን ነው‼️
-------------------------------------------

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️ (Amharic)

የአማኑኤል ልጆች በተገለፁበት ቴሌግራም አድማጮች ላይ በፈጣን ምርጥ ትረዳሚ አሞሌ ብቻ ተሸክመዋል። ይህ ትረዳማዊ አሞሌ ከሆነላችሁ እናመሰግናለን። ይህ አሞሌ በድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወይሰመይ ድጋፍ እናመለከታለን። ይህም በተመረጠው የቴሌግራም እናት ቀንበኛ መጪውን ስታጎበኝ ሊኖረን ነው። ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ ወይሰመይ ስሙ አማኑኤል ዘበ ትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ ላይ መስሀት ተደጋግምባለች። በ ትርጓሜሁ እግዚአብሔር ምስሌነ ይህ አሞሌ በተመረጠው ዝግጅት ወደ ሚቀጥለው እናት አማኑኤል መጪ ስለዚህበሉኝ።

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

18 Jan, 10:50


👉 ከተራ ምንድን ነው?
•••
ከተራ ' ከበበ ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር ፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
••
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ ( ይገድባሉ ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ ( ለጥር 11 ) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡

በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።

በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡

መልካም የከተራ በዓል
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

18 Jan, 10:41


👉 ጾመ ገሀድ
👉 እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ አደረሰን

ጾመ ገሀድ ( ጾመ ጋድ ) ዛሬ ማለትም ቅዳሜ ጥር ፲ የጥምቀት ዋዜማ የከተራ ቀን ጾመ ገሃድ ( ጋድ ) ነው እናም ከጥሉላት ( ከፍስክ ) ምግቦች ጾመን እንዋል።
••
እለቱ ቀዳሚት ሰንበት ( ቅዳሜ ) ስለሆነ በባዶ ሆድ ጾሞ መዋል አይቻልም ነገር ግን ከፍስክ ምግቦች ተቆጥበው ይውሉ ዘንድ በጌታ ፍቅር እናሳስባለን ።
••
በቅዳሜ ቀን ግን መጾም አይገባም ፤ በቅዳሜ ቀን ፀሐይ እስኪገባ መጾም የሚገባ ስራ አይደለም ፤ የሚገባ ጊዜ አለ እንጂ ፤ እስከ ስድስት ያም ባይሆን እስከ ሰባት ። ( ሐይማኖተ አበው ምዕራፍ ፳፩ )
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

13 Jan, 11:15


አባታችን ጻዲቁ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
የአቡዬ ረድኤት፣ በረከትና ጸሎት ከሁላችን ጋር ይሁን
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

12 Jan, 07:09


ጥር 4 - ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
••
ቅዱስ ዮሐንስ ከአስራ ሁለቱ ሐዋርያት መካልከ አንዱ ነው በመጀመሪያ ለደቀ መዝሙርነት የተመረጠው ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ እንድርያስ ጋር  ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ብዙ ስሞች አሉት ፦
••
👉 ጌታ ይወደው የነበረ ሐዋርያ ( ፍቁረ እግዚእ )
💚 ወልደ ዘብዴዎስ
💛 ወልደ ነጎድጓድ
💛 ነባቤ መለኮት ( ታኦሎጎስ )
❤️ አቡቀለምሲስ
❤️ ቁጹረ ገጽ እየተባለ ይጠራል ።
••
ቅዱስ ዮሐንስ ጌታን በመከራው ሰዓት ሳይሸሽ እስከ እግረ መስቀሉ ድረስ የተከተለ ፣ እኛን ወክሎ የእመቤታችንን እናትነት አደራ የተቀበለ ፣ የዕለተ ዓርቡን የጌታን መከራ እያሰበ ቀሪ ዘመኑን በዕንባ የኖረ ሐዋርያ ነው ።
••
ቅዱስ ዮሐንስ እመቤታችንን እየጠበቀ ለ16 ዓመታት ተቀምጧል ከኢየሩሳሌም ርቆ ያልሄደው እርሷን የመጠበቅ አደራ ስለነበረበት ነው ፤ በ49 ዓ.ም እመቤታችን አርፉ እንደ ልጇ በሦስተኛው ቀን ተነስታ ካረገች በኃላ ወደ ኤፌሶን ከተማ ገብቶ አስተምሯል በዚያም በአርጤምስ ቤተ መቅደስ የሚካሄደውን አምልኮ ጣኦት በመቃወሙ በጭካኔው በሚታወቀው በንጉሥ ድምጥያኖስ ዘመን ( ከ81 - 96 ዓ.ም ) በጣኦት አምላኪዎች ተከሶ ለፍርድ በድምጥያኖስ ፊት ቀረበ እርሱም በፈላ ውኃ በተሞላ በርሜል ውስጥ ካሰቃየው በኃላ ወደ ፍጥሞ ደሴት አጋዘው።
••
ቅዱስ ዮሐንስም በጠባብ ዋሻ ውስጥ ለሰባት ዓመታት ( ከ88 - 96 ዓ.ም ) ያህል በግዞት ተቀምጦ ሳለ ነው ራእዩን ያየውና የጻፈው።
••
በ96 ዓ.ም ድምጥያኖስ ሲገደል ቅዱስ ዮሐንስ ከግዞት ተመልሶ ነው ሦስቱን መልእክታቱንና ወንጌሉን የጻፈው።
••
ከሐዋርያት ሁሉ ቀድሞ ሰማዕት የሆነው ታላቅ ወንድሙ ቅዱስ ያዕቆብ ሲሆን ከሐዋርያት ሁሉ ረዥም እድሜ ( 99 ዓመት ) በምድር ላይ የቆየው ሐዋርያ ደግሞ ቅዱስ ዮሐንስ ነው።
••
በመጨረሻም ጌታ በገባለት ቃልኪዳን መሠረት ዮሐ 21 : 22 እንደ ሄኖክና ኤልያስ ሞትን ሳያይ ተሰውሮ ወደ ብሔረ ሕያዋን ተወስዷል።
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

08 Jan, 13:05


👉 የአእላፋት ዝማሬ በድሬዳው
👉 28-4-2017ዓ.ም
👉 በጥቂቱ ይህንን ይመስል ነበር
•••
" በድጋሚ … እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለአምላካችንና ለፈጣሪያችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

08 Jan, 08:11


👉 እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳችሁ ❤️

"… ልዩ ከሆነች ድንግል ማርያም ይህ የአምላክ መወለድ ምን ይደንቅ? ቃልን ወሰነችው። ልደቱንም ዘር አልቀደመውም። በመወለዱም ድንግልናዋን አልለወጠም። ቃል ከአብ ያለ ድካም ወጣ። ከድንግልም ያለ ህማም ተወለደ። ሰብአሰገል ሰገዱለት። አምላክ ነውና ዕጣን አመጡለት። ንጉሥም ነውና ወርቅ አመጡለት። ስለኛ በፈቃዱ ለተቀበለው መዳኛችን ለሆነው ሞቱም ከርቤ አመጡለት። እርሱ ቸርና ሰውን ወዳጅ የሆነ አንድ እርሱ ብቻ ነው። ቅድስት ሆይ ለምኚልን።

"…ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ፤ ለእስራኤልም በበረሀ ውስጥ ከኅቱም አለት ውኃ እንደ ፈለቀ፤ የተደነቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደ አፈራች፤ በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃ እንደ ፈሰሰ ፤ እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደ ነደደች ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም። ለእርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት ክብር ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክልነት ይገባል ለዘላለሙ አሜን።

"…በዓለ ጌናን ስናከብር በሀዘን በመከራ ፣ በጭንቅ ፣ በረሃብና በጥም፣ በሰቀቀን፣ በስደት ፣ በወኅኒ ቤት ፣ በአልጋ ቁራኛ በደዌ ደኛ ፣ በፅኑ ህመም ተይዘው፣ በየቤቱ ፣ በየጎዳናው ፣ በየሆስፒታሉና በፀበል ስፍራዎች ሁሉ ያሉትን ፣ ከሞቀ ቤትና ንብረታቸው ተፈናቅለው በየጥሻው የወደቁትን በማሰብ ፣ በመንከባከብ ፣ በመጠየቅ ፣ በመጎብኘትና ማዕድ በማጋራት ይሁን። ሃገራችን ኢትዮጵያንና ጎረቤቶቿን ፣ መላውንም ዓለም ሁሉ ሰላማዊው ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላም ያድርግልን። አሜን።

"እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለአምላካችንና ለፈጣሪያችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሰን

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

07 Jan, 12:38


እንኳን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት አደረሳችሁ‼️ መልካም በዓል‼️
••
Baga Guyyaa Ayyaana Dhaloota Iyyasuus Kiristoosin Ishin gahe‼️ AYYAANA GAARII‼️
••
እንኳዕ ንባዓል ልደተ ክርስቶስ ብሰላም ኣብፀሐኩም‼️ ርሑስ በዓል ልደት‼️
••
“ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና። ”
ሉቃስ 2፥11
🔔 መልካም በአል 🔔
••••••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

02 Jan, 13:21


👉🏼 የዛሬዋ ቀን የአባታችን የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት የተወለዱበት ቀን ነው እንኳን አደረሳችሁ!
•••
❤️ ነቢይ ናቸው እንደ ነቢያት ትንቢት ተናግረዋልና አባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግን መወለድ አስቀድመው አብስረዋል።
••
❤️ ሐዋርያቸው ናቸው ኢትዮጵያን ከዳር እስከዳር ዞረው ወንጌልን አስተምረዋል።
••
❤️ ሰማዕት ናቸው በድንጋይ እየተወገሩ፣ በብረት በትር እየተደበደቡ፣ በብረት አለንጋ እየተገረፉ፣ በገደል እየተጣሉ ጣዖትን አጥፍተው ወንጌልን አስተምረዋል ለጽድቅም አንድ እግራቸውን ተቆርጠዋል።
••
❤️ ባሕታዊ ናቸው ንጽሕናቸውን ጠብቀው ከዓለም ርቀው በአንድ ዋሻ ተወስነው በቅድስና አሸብርቀው የብሕትውናን ሥነ ሥርዓት ፈጽመዋልና። በረከታቸው ከኛ ጋር ለዘለዓለሙ ይኹን አሜን
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

31 Dec, 09:47


ገብርኤል ማርያምን እንዲህ ብሎ አበሠራት
ለሰላሙ ፍጻሜ የለው በዳዊት መንግሥት
መንበር ላይም መንግሥቱ ስልጣኑ ትፀናለች፡፡

••
በዚህች ዕለት ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ጌታችን እና አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በድንግልና እንደምትወልድ ያበሠራት ዓመታዊ በዓል ነው። የጌታችን ቸርነት ፣ የእመቤታችን አማላጅነትና የመልአኩ ጠባቂነት አይለየን።
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

30 Dec, 09:08


❤️ ቅድስት ድንግል ማርያም
••
የማልከፋው ስላለኝ ሳይሆን አንቺ ስላለሽኝ ነው ፤ በዚህች ምድር የሚያጓጓ ምንም ነገር የለም። ድንግል ሆይ! የአንቺ እናትነት ግን ከሁሉም ይበልጣል ፤ የተወደድሽ እመቤቴ ሆይ! ሰላሜ በአንቺ ነውና ምልጃሽ አይለየኝ! የፈተና ማዕበል ከተነሳባችሁ ፣ ነፍሳችሁ ከተረበሸ ፣ የጭንቀት ዓለት ካጋጠማችሁ እናቴ ማርያም ነይለኝ በሏት! ከልጅሽ ዘንድ አሳስቢን ምህረት እና ይቅርታ እናገኝ ዘንድ ለምኚልን አሜን!
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

27 Dec, 09:02


❤️ ታኅሣሥ 19
❤️
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል
•••
ታኅሣሥ ዐስራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅ ያዳነበት ነው፡፡ ንጉሥ ናቡከደነፆር ከአባታቸው ከይሁዳው ንጉሥ ከኢዮአቄም ጋር የማረካቸው አናንያ፣ ሚሳኤልና አዛርያ እግዚአብሔር በዚህች ዕለት መልአኩን ልኮ ታላቅ ተአምር አድርጎላቸዋል፡፡
••
ንጉሥ ናቡከደነፆር እነዚህን ወጣቶች በቤተ መንግሥቱ ውስጥ ጥበብን እያስተማረ ካሳደጋቸው በኋላ በባቢሎን ሀገሮች ሁሉ ውስጥ ሾማቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሡ የወርቅ ምስል በሠራ ጊዜ መኳንንቱንና በግዛቱ ውስጥ ያሉ ሁሉ ለዚያ ምስል እንዲሰግዱ አዘዘ፡፡ በዚህም ጊዜ ለጣዖቱ ባለመስገድ እግዚአብሔርን ብቻ በማምለክ የጸኑት እነዚህ ሦስት ወጣቶች ብቻ ነበሩ፡፡ ስለ እነርሱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ እንዲህ ተብሎ ነው የተጻፈው፡-
••
‹‹ ንጉሡ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ክንድ ወርዱም ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቁን ምስል አሠራ፤ በባቢሎንም አውራጃ በዱራ ሜዳ አቆመው፡፡ ንጉሡም ናቡከደነፆር መኳንንትንና ሹማምቶችን፥ አዛዦችንና አዛውንቶችን፥ በጅሮንዶችንና አማካሪዎችን፣ መጋቢዎችንም፣ አውራጃ ገዦችንም ሁሉ ይሰበስቡ ዘንድ፣ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ይመጡ ዘንድ ላከ፡፡ በዚያን ጊዜም መኳንንቱና ሹማምቶቹ፣ አዛዦቹና አዛውንቶቹ፣ በጅሮንዶቹና አማካሪዎቹ፣ መጋቢዎቹና አውራጃ ገዦቹ ሁሉ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ምስል ምረቃ ተሰበሰቡ፤ ናቡከደነፆርም ባቆመው ምስል ፊት ቆሙ፡፡ አዋጅ ነጋሪውም እየጮኸ እንዲህ አለ፡- ‹ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የምትናገሩ ሆይ! የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ፣ ተደፍታችሁ ንጉሡ ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቁ ምስል እንድትሰግዱ ታዝዛችኋል፡፡ ተደፍቶም የማይሰግድ በዚያን ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል፡፡› ስለዚህ በዚያን ጊዜ አሕዛብ ሁሉ የመለከቱንና የእንቢልታውን፣ የመሰንቆውንና የክራሩን፣ የበገናውንና የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰሙ ጊዜ፣ ወገኖችና አሕዛብ በልዩ ልዩ ቋንቋም የተናገሩ ሁሉ ተደፉ፤ ንጉሡም ናቡከደነፆር ላቆመው ለወርቅ ምስል ሰገዱ፡፡
••
በዚያን ጊዜም ከለዳውያን ቀርበው አይሁድን ከሰሱ፡፡ ለንጉሡም ለናቡከደነፆር ተናገሩ እንዲህም አሉ ‹ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ፡፡ አንተ ንጉሥ ሆይ የመለከትንና የእንቢልታን፣ የመሰንቆንና የክራርን፣ የበገናንና የዋሽንትን፣ የዘፈንንም ሁሉ ድምፅ የሚሰማ ሰው ሁሉ ተደፍቶ ለወርቁ ምስል ይስገድ፤ ተደፍቶም የማይሰግድ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ይጣላል ብለህ አዘዝህ፡፡ በባቢሎን አውራጃ ሥራ ላይ የሾምሃቸው ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም የሚባሉ አይሁድ አሉ፤ ንጉሥ ሆይ! እነዚህ ሰዎች ትእዛዝህን እንቢ ብለዋል፤ አማልክትህን አያመልኩም፥ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል አይሰግዱም፡፡› ናቡከደነፆርም በብስጭትና በቍጣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም ያመጡ ዘንድ አዘዘ፤ እነዚህንም ሰዎች ወደ ንጉሡ ፊት አመጡአቸው፡፡ ናቡከደነፆርም ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ሆይ! አምላኬን አለማምለካችሁ ላቆምሁትም ለወርቁ ምስል አለመስገዳችሁ እውነት ነውን? አሁንም የመለከቱንና የእንቢልታውን የመሰንቆውንና የክራሩን የበገናውንና የዋሽንቱን የዘፈኑንም ሁሉ ድምፅ በሰማችሁ ጊዜ ተደፍታችሁ ላሠራሁት ምስል ብትሰግዱ መልካም ነው፤ ባትሰግዱ ግን በዚያ ጊዜ በሚነድድ እሳት እቶን ውስጥ ትጣላላችሁ፤ ከእጄስ የሚያድናችሁ አምላክ ማን ነው?›› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም መለሱ ንጉሡን ‹ናቡከደነፆር ሆይ! በዚህ ነገር እንመልስልህ ዘንድ አስፈላጊያችን አይደለም፡፡ የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፤ ከእጅህም ያድነናል፡፡ ነገር ግን ንጉሥ ሆይ! እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ› አሉት፡፡
••
የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም ላይ ቍጣ ሞላበት፡፡ የፊቱም መልክ ተለወጠባቸው፡፡ እርሱም ተናገረ የእቶንም እሳት ይነድድ ከነበረው ይልቅ ሰባት እጥፍ አድርገው እንዲያነድዱት አዘዘ፡፡ ሲድራቅንና ሚሳቅንም አብደናጎንም ያስሩ ዘንድ ወደሚነድድም ወደ እቶን እሳት ይጥሉአቸው ዘንድ በሠራዊቱ ውስጥ ከነበሩት ኃያላን አዘዘ፡፡ የዚያን ጊዜም እነዚህ ሰዎች ከሰናፊላቸውና ከቀሚሳቸው ከመጐናጸፊያቸውም ከቀረውም ልብሳቸው ጋር ታስረው በሚነድድ በእቶን እሳት ውስጥ ተጣሉ፡፡ የንጉሡም ትእዛዝ አስቸኳይ ስለሆነ የእቶኑም እሳት እጅግ ስለሚነድድ፣ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም የጣሉአቸውን ሰዎች የእሳቱ ወላፈን ገደላቸው፡፡ እነዚህም ሦስቱ ሰዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም ታስረው በሚነድደው በእቶኑ እሳት ውስጥ ወደቁ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ናቡከደነፆር ተደነቀ ፈጥኖም ተነሣ፤ አማካሪዎቹንም ‹ሦስት ሰዎች አስረን በእሳት ውስጥ ጥለን አልነበረምን?› ብሎ ተናገራቸው፡፡ እነርሱም ‹ንጉሥ ሆይ! እውነት ነው› ብለው ለንጉሡ መለሱለት፡፡ እርሱም ‹እነሆ እኔ የተፈቱ በእሳቱም መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ፤ ምንም አላቈሰላቸውም፤ የአራተኛውም መልክ የአማልክትን ልጅ ይመስላል› ብሎ መለሰ፡፡ የዚያን ጊዜም ናቡከደነፆር ወደሚነድደው ወደ እሳቱ እቶን በር ቀርቦ ‹እናንተ የልዑል አምላክ ባሪያዎች ሲድራቅና ሚሳቅ አብደናጎም! ኑ ውጡ› ብሎ ተናገራቸው፡፡ ሲድራቅና ሚሳቅም አብደናጎም ከእሳቱ መካከል ወጡ፡፡
••
መሳፍንቱና ሹማምቶቹም አዛዦቹና የንጉሡ አማካሪዎች ተሰብስበው እሳቱ በእነዚያ ሰዎች አካል ላይ ኃይል እንዳልነበረው፣ የራሳቸውም ጠጕር እንዳልተቃጠለች ሰናፊላቸውም እንዳልተለወጠ፣ የእሳቱም ሽታ እንዳልደረሰባቸው አዩ፡፡ ናቡከደነፆርም መልሶ ‹መልአኩን የላከ ከአምላካቸውም በቀር ማንም አምላክ እንዳያመልኩ ለእርሱም እንዳይሰግዱ ሰውነታቸውን አሳልፈው የሰጡትን የንጉሡንም ቃል የተላለፉትን በእርሱ የታመኑትን ባሪያዎቹን ያዳነ፣ የሲድራቅና የሚሳቅ የአብደናጎም አምላክ ይባረክ፡፡ እኔም እንደዚህ የሚያድን ሌላ አምላክ የለምና በሲድራቅና በሚሳቅ በአብደናጎም አምላክ ላይ የስድብን ነገር የሚናገር ወገንና ሕዝብ በልዩ ልዩም ቋንቋ የሚናገሩ ይቈረጣሉ፣ ቤቶቻቸውም የጕድፍ መጣያ ይደረጋሉ ብዬ አዝዣለሁ› አለ፡፡ የዚያን ጊዜም ንጉሡ ሲድራቅንና ሚሳቅን አብደናጎንም በባቢሎን አውራጃ ውስጥ ከፍ ከፍ አደረጋቸው፡፡›› ትንቢተ ዳንኤል 3፡1-30፡፡
••
ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም መልአኩ በአማላጅነቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

25 Dec, 09:14


❤️ ኪዳነ ምህረት
••
ርግብየ ርግብየ እያለ የሚያመሰግንሽ የጥበበኛው ሰሎሞን ርግብ ነሽና ድንቁርና ረኃብ እንዳይጸናብኝ እህል ጥበብን መግቢኝ። እመቤቴ ሆይ ፤ኀጥእን ለጥፋት የማይመኝ ቂም በቀልን የማያውቅ ልብሽ ፍጹም የዋህ ነው።
••
ስለዚህ ይቅርታ ልማድሽ ነውና ይቅር በይኝ፡፡ በልቤ ውስጥ ያለውን ምኑን ስንቱን እነግርሻለሁ? ኅዘኔን ጭንቀቴንም አንች ታውቂዋለሽና፡፡ መልክአ ኤዶም Rየኪዳነምህረት ምልጃ አይለየን🙏
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

21 Dec, 04:33


❤️ ቅዱስ ሚካኤል
•••
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ሆይ! የተጨነቁትን ዘውትር እንደምትረዳቸው ሁሉ እኛንም ለመርዳት ክንፍህን ዘርግተህ ፈጥነህ ድረስልን።
•••
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ምልጃው ጥበቃና በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን‼️
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

07 Dec, 08:56


❤️ አማኑኤል ሆይ
••
በክንፍህ መዘርጋት ይህን ትውልድ አንተ ጋርድ። በዚህ ዓለም ሹሞች ሳይሆን ማመኔን በአንተ አድርግልኝ። ልቤን በአንተ አሳርፍልኝ! ከሰንበት ረድኤት በረከት ያሳትፈን እግዚአብሔር አምላካችን አሜን!
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

29 Nov, 09:49


❤️ ህዳር 21 አክሱም ጽዮን ማርያም
❤️ እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ

••
ህዳር 21 ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል ነው ብለን በተለየ መልኩ የምናከብርበት ምክንያት፦
••
👉🏼 ታቦተ ጽዮን በምርኮ በሄደችበት በሀገረ ፍልስጤም ዳጎን የተባለ የአህዛብን ጣኦት አድቅቃ በድል የተመለሰችበትን ዕለት በማሰብ። ታቦተ ጽዮን ንጉሥ ሰሎሞን ወደ ሠራላት ቤተመቅደስ በክብር የገባችበትን ዕለት በማሰብ፤
••
👉🏼 የቀደሙ ነብያት ስለእመቤታችን በተለያየ አምሳል ያዩበት ለምሳሌ፦ ነብዩ ዕዝራ በሃገር መንፈሳዊት፣ ሕዝቅኤል በተዘጋች ቤተመቅደስ፣ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ ወዘተ ያዩበትን ዕለት በማሰብ፤
••
ቀዳማዊ ምኒሊክ ከዐሥራ ሁለቱ ነገድ እስራኤል የበኩር ልጅ ጋር ሊቀ ካህናቱን አዛሪያስንና ታቦተ ጽዮንን ይዞ አክሱም የደረሰበትን ዕለት ለማሰብ፤
••
👉🏼 በአብርሃ ወአፅብሃ ዘመነ መንግስት ክርስትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ አዋጅ የታወጀበትን በማሠብ፤
••
👉🏼 አብርሃ ወአጽብሃ በወርቅና በዕንቁ ያሠሩት ባለ አሥራ ሁለት ክፍል ቤተ መቅደስ ለመጀመሪያ ጊዜ ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት ዕለት በመሆኑ፤ በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አብያተ ክርስቲያንን ስታቃጥል ታቦተ ጽዮንን ይዘው ወደ ዝዋይ ሀይቅ ከተሰደዱ በኋላ ዘመነ ሰላም ሲጀመር አክሱም በነበሩ ካህናት አስታዋሽነት ከዝዋይ ወደ አክሱም የገባችበት ዕለት በመሆኑም በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ከፍ ባለ መንፈሳዊ በዓል እናከብራለን። ከእመቤታችን ረድኤትና በረከት ይክፈለን!!!
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

28 Nov, 09:01


❤️ ቅዱስ ገብርኤል አባቴ
••
ቅዱስ ገብርኤል አባቴ ከአምላካችን ከእየሱስ ክርስቶስ ምህረትና ቸርነትን ለምንልን አማልደል ፤ የራማው መላአክ ገብርኤል ከመጣብን ክፉ መቅሰፍት በምልጃህ ጠብቀን ይቅርታውን ምህረቱን ይልክልን ዘንድ ለምንልን አሜን! 🙏🏿
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

25 Nov, 12:29


የጠፋው በግ ተገኝቷል እና እንኳን ደስ አላችሁ
••
#ዘማሪ_ሐዋዝ_ተገኝ ስንጠብቅህ የነበረ ወንድማችን ወደ ቤትክ እንኳን ደህና መጣህ የእናት እጅ ልጆቿን ለማቀፍ ትናፍቃለች
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

25 Nov, 10:56


የቀድሞው ዘማሪ ሐዋዝ ተገኝ ወደ ቀደመው የአባቱ ቤት ወደሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት መቅደስ ተመልሷል
••
በተ*ዶሶ እንቅስቃሴ ላይ የነበረው የቀድሞ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዘማሪ የነበረው ሐዋዝ ተገኝ ቀድሞ ያገለግልባት ወደነበረችው ቅድስት እና ንጽሕት ወደሆነችው ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ መቅደስ በንሰኃ ጥምቀት ተመልሷል።
••
በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ - ጃን ማዕተብ በኩል 70 ወጣቶች ወደ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን በልጅነት ጥምቀትና በቄደር ጥምቀት ተመለሱ:: ጃን ማዕተብ ሥራ ከጀመረ ጊዜ አንሥቶ በአንድ ለአንድ (የገፅ ለገፅ) የትምህርት መንገድ የተማሩት እነዚህ ንዑሰ ክርስቲያን ከእስልምና ከፕሮቴስታንት ከካቶሊክ እና እምነት የለሽነት የተመለሱ መሆናቸውን የጃን ማዕተብ የንዑሰ ክርስቲያን ክትትል አስተባባሪ ዶ/ር ቤተልሔም ገልጻለች::
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

25 Nov, 09:59


፪. ጾመ ነቢያት:- ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገለጦ ስለታያቸው፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች: ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም: ቅዱስ ሙሴ: ቅዱስ ኤልያስ፣ ቅዱስ ዳንኤል ና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: (ዘዳ 9:19, ነገ. 19:8, ዳን. 9:3፣ መዝ. 68:10, 108:24) ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ: ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል:: ለሞትም አብቅቶታል::
••
፫. ጾመ ሐዋርያት:- ሐዋርያት ‹‹ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን፣ ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?›› ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡
••
፬. ጾመ ማርያም:- እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና ‹‹ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?›› ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና ‹‹ጾመ ማርያም›› ይባላል፡፡
••
፭. ጾመ ፊልጶስ:- ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት፤ አስክሬኑ ከደቀመዛሙርቱ ስለተሰወረ፤ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል፤ ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡
••
፮. ጾመ ስብከት:- የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት፥ የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት፥ የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡
••
፯. ጾመ ልደት:- የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት ስለሆነ ‹‹ጾመ ልደት›› ይባላል፡፡
••
ጾምን ትእዛዝ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የፍቅርና የበረከት ምንጭ በመሆኑ ጭምር ደስ እያለን ብንጾመው የቅዱሳኑ በረከት ያድርብናል፡፡
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

25 Nov, 09:58


" እንኳን ለጾመ ነቢያት በሰላም እና በጤና አደረሳችሁ "
••
ይህ ፆም ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ ፆሞች ውስጥ አንዱ ሲሆን አበው ነብያት የጌታችን የመድሃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መውረድ መወለድ በትንቢት መነፅር እየተመለከቱ የፆሙት ታላቅ ፆም ነው። ዛሬም እኛ ክርስቲያኖች የአባቶቻችንን ፈለግ ተከትለን በፆምና በፀሎት ወቅቱን በማሳለፍ ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን ዝቅ አድርጎ ወደ አለም መምጣቱንና የዓለም ቤዛ መሆኑን የምናስብበት ነው። ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤ በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡፡ እነርሱም፤
••
፩. ጾመ አዳም:- አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገት ከተባረረ በኋላ; በፈጸመው በደል አዝኖ ፥ ተክዞ፤ አለቀሰ (እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ፤ እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ) ፥ ጾመ፣ ጸለየ፡፡ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ ‹‹ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ፣ በደጅህ ድኼ፣ በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ፣ ሞቼ አድንሃለሁ፡፡›› የሚል ነው፡፡ /ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ/ ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ ፥ የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት ‹‹ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡
••

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

20 Nov, 17:05


ቅ/ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (ከበዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ ኅዳር 13 ( የአእላፍ መላእክት ) በዓል ድረስ ከአምላኩ ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት ዕለታት ናቸው፡፡
•••
እስራኤልን ከግብጽ ባርነት እየመራቸው ማውጣቱን የሚዘከርበት በዓል ነው፡፡ ይህም የሆነው ያዕቆብ በረሃብ 70 ኹኖ ወደ ግብፅ ከወረደ በኋላ ከ215 ዓመታት (አብርሃም ወደ ግብፅ በተሰደደ ከ430 ዓመታት) በኋላ፤ የዮሴፍን ዝና ያልሰማ፥ ዮሴፍን የማያውቅ ፈርዖን በግብፅ ነገሠ፡፡  እስራኤል ከእኛ ይልቅ በዝተዋል ጠላቶቻችን ቢነሱብን ከጣለቶቻችን ጋር ተደርበው ያጠፉናል በማለት አገዛዝ አጸናባቸው ፥ ፍርድ አጓደለባቸው፡፡
•••
የእስራኤል ሴቶች ልጅ ሲወልዱ ወንድ ከሆነ እንዲገደል በማድረግ መከራ አጸናባቸው፡፡ ለ215 ዓመታት በግብፅ በባርነት ከቆዩ በኋላ ከዕብራውያን ወገን የሆነችው ራሔል ጭቃ እያቦካች ምጥ በያዛት ጊዜ ከሥራዋ እንዲያሳርፏት ጠየቀች ፤ ግብጻውያን ግን የሕፃናቱ ደም ጡቡን ያጠነክራል ርገጭ  አሏት፡፡ ከማሕፀኗ የወጡ ሁለት መንትያ ልጆቿን እያየች ከጭቃ ጋር ረገጠች ፤ ራሔልም መሪር ልቅሶን አለቀሰች ፤ ስለ ልጆቿም መጽናናትን እንቢ አለች፡፡
•••
የእስራኤል ንጉሥ ሆይ የሆነብንን እይ ስትል ራሷን ይዛ ታለቅስ ጀመር ፥ እንባዋንም ወደ ሰማይ ንጉሥ ወደ እግዚአብሔር ረጨች፡፡ የራሔል እንባዋ የሕዝበ እስራኤልን ሁሉ ጩኸት ፥ እሮሮ ይዛ ቅድመ እግዚአብሔር ደረሰች፡፡ “. . . ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች የሉምና ስለ ልጆቿ መጽናናት እንቢ አለች” /ኤር 31፥5፤ ማቴ 2፥17/ እንዲል፡፡
•••
ከዚህ በኋላ እግዚአብሔር ሙሴን አስነሳና፤ በሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል መሪነት፤ 10 ተዓምራትን በምድረ ግብፅ በ11ኛ ተዓምር ደግሞ በኅዳር 12 ( ፈርዖንን ከነሠራዊቱ በኤርትራ ባሕር አስጥሞ ) ወደ ተስፋይቱ ምድረ መራቸው፡፡   ባሕረ ኤርትራን እስራኤላውያን እንደተሻገሩም የእስራኤል ልጆች የሙሴ የአሮን እኅት ማርያም ከበሮ እየመታች ‹‹ ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ ፤ እግዚአብሔር ተዋጊ ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው እያሉ፡፡ ››
•••
ጠላታቸውን የመታላቸውን ፥ እነሱንም በተአምራቱ ያሻገራቸውን ፥ ከጠላታቸው እጅ ያዳናቸውን እግዚአብሔርን አመሰገኑ፡፡ ከዚህ በኋላ መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ሚካኤል እየመራቸው ፥ መና ከሰማይ እያወረደላቸው ፥ ውሃ ከጭንጫ እያፈለቀላቸው ፥ ቀኑን በደመና ፥ ሌቱን በብርሃን መርቷቸው አርባ ዘመን ተጕዘው የቃል ኪዳን አገራቸው ምድረ ርስት ከነዓንን ( የዛሬዋ ኢየሩሳሌምን ) ወርሰዋል፡፡ /ዘጸ. 15/
•••
ከሙሴ በኋላ እስራኤልን የመራው ነቢዩ ኢያሱም እስራኤልን በሚመራበት ጊዜ ሊቀ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እስራኤልን ይረዳቸው ነበር፡፡ ከጠላቶቻቸው ጋር ሲዋጉም ሰልፉን ይመራ የነበረው ቅዱስ ሚካኤል ነበር፡፡ ለምሳሌ እስራኤላውያን ከኢያሪኮ አጠገብ በነበሩበት ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል ተገልጦ ኢያሱን አነጋግሮታል፡፡
•••
ኢያሱ በኢያሪኮ አጠገብ ሳለ ቀና ብሎ ሲመለከት የተመዘዘ ሰይፍ በእጁ የያዘ አንድ ሰው ከፊቱ ቆሞ አየ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦ “ከእኛ ወገን ነህ ወይስ ከጠላቶቻችን?” ሲል ጠየቀው፡፡ እርሱም “አይደለሁም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ በመሆኔ መጥቻለሁ” ብሎታል /ኢያሱ 5፥13-15/፡፡
•••
ይህ የተመዘዘ ሰይፍ ይዞ ከኢያሱ ፊት ለፊት የቆመው መልአክ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል (እንዲሁም መልአኩ ቅዱስ ራጕኤል) ነው፡፡ ይህን ለአብነት አነሣን እጅ እስራኤል በሚበድሉበት ጊዜ ሁሉ ወደ እግዚአብሔር የሚማልድላቸው ይህ ታላቅ መልአክ መጋቤ ብሉይ ቅ/ሚካኤል ነበር ፤ እግዚአብሔር አምላክ በእደ መልአኩ ይጠብቀን ፤ ከበዓሉ ረድኤት ፥ በረከት ይክፈለን ፤ አሜን
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

20 Nov, 16:18


እንኳን ለቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ በዓል በሰላምና በጤና
አደረሳችሁ አደረሰን ‼️
💚💛❤️
ወበዓለ መራኄ ፍኖቱ ለቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
•••••••••
ኅዳር ፲፪ ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ ፥ በእግዚአብሔር የጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ ለምስጋና የሚቆም፥ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ፥ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሢመቱና እስራኤላውያንን በባሕረ ኤርትራ ያሸገረበት በዓል ነው፡፡
•••
በዓለ ሢመቱ ፤ ሚካኤል ማለት ማን እንደ እግዚአብሔር ማለት ነው፡፡ ከሌሎች መላእክት ጋር በእለተ እሑድ ካለመኖር ወደ መኖር አምጥቶ የተፈጠረ ሲሆን፤ እርሱም መጀመሪያ ከ100ው ነገደ መላእክት የ10ሩ ነገደ መላእክት (የኃይላት) አለቃቸው ነበር፤ በተጨማሪም ከሳጥናኤል ውድቀት በኋላ የኃይላት አለቅነቱን እንደያዘ የአጋእዝትን ነገድም ( ሳጥናኤል/ሰማልያል/ ) ይመራቸው የነበሩትን 10 ነገዶችም በአለቅነት ደርቦ አለቃ ኾኗል ፤ እንዲሁም በዛሬው ዕለት ለ100ውም ( 99ኙም ) ነገደ መላእክት (ለእልፍ አእላፋት መላእክት) አለቃቸውም ቅዱስ ሚካኤል ኾኖ የተሾመበት ዕለት ነው፡፡ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡
•••
ቅ/ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 (ከበዓለ ሢመቱ) ጀምሮ እስከ ኅዳር 13 ( የአእላፍ መላእክት ) በዓል ድረስ ከአምላኩ ለፍጥረታት ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት ዕለታት ናቸው፡፡
•••

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

15 Nov, 14:16


እንኳን ለበዓለ ደብረ ቁስቋም በሰላም አደረሰን /አደረሳችሁ
💚💛❤️
እመቤታችን ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ጋር ከስደት ወደ ሀገሯ
የተመለሰችበት ቀን ነው
••••••••
ህዳር 6 በዚህች ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ አንዲሁም ከዮሴፍና ሶሎሜ ጋር 3 ዓመት ከ 6 ወር በስደት ከተንገላታች በኋላ ወደ አገራቸው የተመለሱበት ቀን ነው ፤ ከግብጽ ሲመለሱ ጌታችን በእመቤታችን ጀረባ ላይ ሆኖ እነዚያ እውራንን ባበሩ ጣቶቹ ወደ ኢትዮጵያ ይጠቁም ያመለክት ነበር
••
እመቤታችንም ልጄ ሆይ ለምንድነው ጣትህን የምታመለክተው ብትለው "ያቺ የተባረከች አገር ናት እኔን የሚያመልኩ አንቺን የሚማልዱ በፍቅርሽ የነደዱ ቅዱሳን መነኮሳት የሚፈልቁባት አገር ናት ፤ ያንቺ ዘመዶች ሰቅለው ይገድሉኛል በዚህች አገር ያሉ ግን ሳይዩኝ ያመኑኛል ፤ አስራት በኩራትሽ ትሁን ብሎ ሰጥቷታል፡፡ በኪደተ እግራቸውም ጣና ሐይቅን ፤ ዋልድባንና ሌሎችንም ቦታዎች ዞረው እንደባረኩ ድርሳነ ኡራኤልና ተአምረ ማርያም ላይ በስፋት ተጽፏል፡፡
••
እመቤታችንን ከሐና ማህጸን ፈጥሮ ከፍጥረተ ዓለም ለይቶ ከሁሉ አልቆ የእናት አማላጅ ትሁናችሁ ብሎ የሰጠን እግዚአብሔር ይመስገን።
••
ቁስቋም ማርያም - እናቴ ማርያም ምልጃሽና ምህረትሽ አይለየን አሜን!
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

10 Nov, 13:03


❤️ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ እንወድሻለን‼️
••
ሰላም ለኪ አምላክን የወደለድሽ በስጋም በነፍስም ድንግል የሆንሽ ከልጅሽ ዘንድ አሳስቢልን ምህረትና ይቅርታ እናገኝ ዘንድ ለምኚልን
••
ልደታ ማርያም  በዕለተ ቀኗ ጨለማውን ብርሃን ሃዘናችንን በደስታ ትቀይርልን አሜን
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

07 Nov, 04:25


እንኳን ለአምላክ ወሰብእ ለቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ በዓል አደረሰን።
••
ጥቅምት 28 || " የምስራቁ ነፋስ አንበጣዎችን አመጣ። " ዘጸአት 10፤13
••
የበዓሉ መሰረትና ታሪክ ይህ ነው በወርሐ ጥቅምት እንዲህ ሆነ በሱዳን በኩል የመጣ አንበጣ የኢትዮጵያን ምድር ከል መስሎ ወረሳት የተዘራው ሳይሰበሰብ  የአንበጣ እራት ሊሆን ሆነ። ንጉሠ ሸዋ ሣህለ ሥላሴ
ወደ ታላቁና ተአምረኛው ሚጣቅ ቅዱስ አማኑኤል  ደብር ሄደው እንባቸውን በእጃቸው አቁተው አዝነው  ቅዱስ አማኑኤል ፈጣሪዬ አምላኬ ሆይ የመጣው የአንበጣ መንጋ ከጠፋ ሕዝቤ ከሰቀቀን ድኖ የዘራውን አጭዶ ከጎተራ ከገባ በአዋጅ ነጋሪት ጎስሜ ቀንደ መለከት አስነፍቼ ድብ አንበሳ ነጋሪት አስመትቼ ታቦትህን በካህናቱ አስወጥቼ አከብራለሁ ብለው ስዕለት ያደርጋሉ የአንበጣው መንጋ ሰማይ ያርግ ምድር ይስረግ ሳይታወቅ አንድ ሰብል ሳያጠፋ ከኢትዮጵያ ምድር ይጠፋል በዓሉም በዚያ ምክንያት ተጀመረ የአባቶቻችን ስም ላለመጥራት ታሪክ አናድበስብስ መሰረቱ ይህ ነው።
••
በበዓሉ የሚከብረው ስሙ የሚወደሰውም  ወሰብእ ቅዱስ አማኑኤል ነው ቸርነቱ የተገለጠበት ተአምራቱ የታየባት እምርት እለት። በአባቶቻችን መዲና አዲስአበባ መርካቶ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ደብር ሁላችንም ተገኝተን እናክብር።
••
አምላካችን በቸርነቱ ይመልከተን ምድራችንን የወረረውን የዘረኝነት አንበጣ ያጥፋልን በየልቦናችን ያቆምነውን የዘረኝነት ጣኦት በኃይለ መለኮቱ ያቅልጥልን አስተዋይ ለሕዝብ የሚያስብ መሪ አይንሳን እኛንም ገባርያነ ሰላም ያድርገን ከዘረኝነት ደዌ ከፍቅር ረሐብ ከዝሙት እሳት ከክሕደት አሽክላ ይሰውረን በፈቃዳቸው ላበዱ ፈውስን ብረት ላነሱ ትዕግስቱን ያድልልን አሜን አሜን አሜን

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

06 Nov, 09:14


ዛሬ ጥቅምት 27 ቀን የመድኃኔዓለም የስቅለት በዓል በደማቁ ይከበራል። እንኳን ለፈጣሪያችን መድኃኔዓለም እየሱስ ክርስቶስ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
••
ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም እውነት ነው ፤ እራስን ነፍስን አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ድንቅ ነገርና ምን ድንቅ ፍቅር አለ? መድኃኒታችን ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና በቸርነቱ ስለሁላችን ድኀነት ሲል ራሱን ወዶና ፈቅዶ ለሞት አሳልፎ በመስጠት ፍጹም ፍቅሩን አሳይቶናል። ቸሩ መድኃኔዓለም በምህረቱ ይጎብኘን ዘንድ ቅዱስ ፍቃዱ ይሁን አሜን!
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

02 Nov, 14:42


❤️ ፍጡነ ረድኤት ቅዱስ ጊዮርጊስ
••
ኃያሉ ሰማዕት ሆይ እኔን ምስኪኑን አገልጋይህን ከሃይማኖት መራቆት ከምግባር እጦት ታድነኝ ዘንድ እማልድሃለሁ ••• ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈጥኖ ደራሽ በመከራ ጊዜ ፈጥኖ ይድረስልን አጥንታችንን ለመፍጨት ደማችንን ለማፍሰስ የተነሱትን ቅዱስ ጊዮርጊስ ያፍዝዝልን ሃገራችንን ሰላም ያድርግልን የማታንቀላፋው ትጉህ እረኛችን ጠብቅልን ቅድስት ሃገራችንን
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

01 Nov, 09:24


❤️ መልዐኩ ቅዱስ ዑራኤል
••
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ ከወዳጇ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከእየሱስ ክርስቶስ ጋር ወደ ግብጽ ስትሰደድ መንገድ እየመራ ፤ ከእስራኤል ወደ ግብጽ ከዚያም ከእመቤታችን ጋር በሀገራችን ኢትዮጵያ እየመራ ያመጣት መልአክ ነው።
••
ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለዓለም ቤዛ ሆኖ በተሰቀለበት ጊዜ ፥ ክቡር ደሙ በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃን ነሳንስ የረጨው እሱ ነው። ለነብዩ ዕዝራ ሱቱኤል ጽዋ ልቦና ያጠጣው ፥ ጥበብን ማስተዋልን የሰጠው የጠፉ መጽሓፍት በቃሉ አስታውሶ እንደገና ያጻፈው የረዳው መልአክ ነው።(ዕዝ፲፫፥፴፱)
••
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ትዕዛዝ ብዙ ድርሰት የደረሱት መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ጽዋ ህይወት ስላጠጣቸው ነው።
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

31 Oct, 13:35


እመብርሃን ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም
••
እለት እለት አፌን ሞልቼ የጌታዬን እናት እመቤቴን ሳመሰግናት ልቤ ደስ ይሰኛል ፤ በእሷ የተጎበኘ የተደረገለት ደግሞ ክብሯን የበለጠ ከፍ ያደርጋል። ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደር አሜን!
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

29 Oct, 08:13


❤️ የምትጠብቀኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሆይ‼️
••
ከዲያብሎስና ከዓለም ጋር በማደርገው ውጊያ ፈጥነህ ደርሰህ አድነኝ፤ አእምሮዬን አብራልኝ። ኃጢአትን እንድንቅ፣ በማንም ላይ እንዳልፈርድና ከክፉ ስራዎች ሁሉ እንዳልተባበር ጠብቀኝ። በችግሬ ግዜም ኃይልህና እርዳታህ አይለየኝ።
••
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል በምልጃው ከክፉ ሁሉ ነገር ይጠብቀን አሜን!
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

27 Oct, 08:38


❤️ ቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ
(ጥቅምት 17)
••
ዛሬ ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ አመታዊ በዓል ነውሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ ከሰባት ዲያቆናት መካከል በቅድስና ሕይወቱ ለክርስትያኖች ዓብነት የሆነው ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ይገኝበታል
••
እስጢፋኖስ ማለት 'መደብ' ማለት ሲሆን በግሪክ ቋንቋ 'አክሊል' ማለት ነው።
••
ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ትውልዱ ከነገድ ብኒያም ሲሆን አባቱ ስምዖን እናቱ ሐና ይባላሉ ።
የሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ረድኤት በረከት አይለየን
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

25 Oct, 20:23


❤️ #ኪዳነምህረት የምህረት እናት‼️
••
የሁሉንም እንባ አባሽ፣ የሃዘኔ ደራሽ፣ የጭንቅ አማላጄ፣ ሳዝን መፅናኛዬ፣ ስደክም ጉልበቴ፣ በቃልኪዳንሽ ጠብቂኝ አሜን!
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

24 Oct, 09:06


እንኳን ለአባታችን አቡነ አረጋዊ አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
•••
❤️ #አቡነ_አረጋዊ_ዘደብረ_ዳሞ
•••
በሃገራችን ስም አጠራራቸው ከከበረ አባቶች አንዱ እኒህ ጻድቅ ናቸው። በ5ኛው ክ/ዘ ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ ሆነው ወደ ኢትዮጵያ መጡ፡፡ አቡነ አረጋዊ መጨረሻቸውን በደብረ ዳሞ፣ ትግራይ ቢያደርጉትም በወሎ፣ በጎንደር፣ በጎጃም፣ በሸዋና በደቡብ ታሪክ ውስጥ ግን አሉ፡፡ ደቡብ ጎንደር ውስጥ ጥንታዊው ገዳማቸውና የዝማሬ መዋሥዕት ማስመስከሪያው ዙር አባ አረጋዊ አለ፡፡
•••
ጣና ቂርቆስ፣ አዲስ አበባ አጠገብ የሚገኘው የረር፣ እንዲያውም ከዚያ ተሻግሮ ጋሞጎፋ የምትገኘው ብርብር ማርያም ታሪካቸውን ከእርሳቸው ጋር ያገናኛሉ፡፡ የአቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን የሀገሪቱ ድንበር ጠባቂ ሆኖ ሞያሌ ላይም ይገኛል፡፡
•••
ደብረ ዳሞ በሰሜን ኢትዮጵያ፣ ትግራይ በ535 ዓ.ም. የታነፀ ገዳም ነው፡፡ መጠርያ ስሙንም ያገኘው ከአምባው ሲሆን፣ ከባሕር ወለል 2216 ሜትር ከፍታ ላይ ይገኛል፡፡ ደብረ ዳሞ ገዳም እስካሁን ህልውናው የተጠበቀ ከ1400 ዓመት በላይ ዕድሜ አስቆጥሯል፡፡
•••
ደብሩን ለማየት ማናቸውም ሰው ወደ ደብሩ ሲወጣ ርዝመቱ 16 ሜትር ከሆነው ገመድ ተንጠልጥሎ ከላይ ተስቦ ይወጣዋል፡፡ “የሊፍት” ፍልስፍና በደብሩ መነኮሳት የታቀደ ይመስላል፡፡ በገድል በቱሩፋት 99 ዓመት ከቆዩ በኋላ ጥቅምት 14 እንደ ሄኖክ እንደ ኤልያስ እንደ ፍቁረ እግዚ ዮሐንስ ተሰውረዋል:: የአባታችን የአቡነ አረጋዊ ረድኤት በረከት አይለየን !
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

16 Oct, 16:49


👉🏼 ሥማችን እና ግብራችን ለየቅል ለሆነብን ለእኛ አጭር መልዕክት
👉🏼 ከመጋቢ አዲስ እሸቱ
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

11 Oct, 08:51


❤️ ድንግል ሆይ ልደትሽ ልደታችን ነው‼️
••
እነሆ የብርሃናት ንጉስ ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስን ለመውለድ የብርሃን እናት ቅድስት ድንግል ማርያም በእውነት ተወለደች፤
••
ከሊባኖስ ተራሮች ርግብ ጸዐዳ ተወለደች፣ በሔዋን ምክንያት የተዘጋው የሕይወት መንገድ ይከፈትልን ዘንድ የሕይወት እናት ተወለደች፤
••
የአለም ብርሃን ኢየሱስ ክርስቶስን ከእርሷ ይወለድ ዘንድ እመብርሃን ዛሬ ተወለደች፤
••
ኢያቄምና ሐና ዳግሚት ሰማይ ተብላ የተጠራችውን ድንግልን ወለዱ ፤ እውነተኛው ፀሐይ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርሷ ይወለድ ዘንድ እመ ፀሐይ ( የፀሐይ እናት ) ቅድስት ድንግል ተወለደች፤
••
ብርሃንን ለማስገኘት መወለድ መታደል ነው ፣ ከሰው ልጆችም መካከል መመረጥ ዕፁብ ድንቅ ነው ፤ የመድኃኒአለም እናት ለመሆን መወለድ ሰማያዊ ፀጋ ነው።
••
በእውነት እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእግዚአብሔር ስጦታ ናት!
••
የእናታችን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ፍቅሯ ፣ አማላጅነቷ፣ ጥበቃዋ ፣ በረከቷ ፣ ረድኤቷ ፣ ይደርብን
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

08 Oct, 08:53


❤️ የድንግል ልጅ አማኑኤል ይጠብቀን አሜን
••
አማኑኤል ሆይ - በክንፍህ መዘርጋት ይህን ትውልድ አንተ ጋርድ። በዚህ ዓለም ሹሞች ሳይሆን ማመኔን በአንተ አድርግልኝ። ልቤን በአንተ አሳርፍልኝ!! ለተጨነቁ መጽናናትን ፣ ለተረበሹ ሰላምን ፣ ላጡት ማግኘትን ፣ ለታመሙት ምህረትን ይስጥልን አሜን!
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

07 Oct, 10:23


እረኛዬ መድኃኔዓለም
••
ጥቂት ስምህን ማወቅ ብዙ መረጋጋትን ታጎናጽፋለች ፤ በተሳዳቢ ዓለም ዝምታን አስተማርከኝ። እየተገፉ መደሰትን ፣ እያጡ ማመስገንን ፣ ነገን እያሳይህ ዛሬ ማኖርን ፣ ባንተ ማረፍን በስምህ ተማርኩ። መድኃኔዓለም እረኛዬ የምታሳጣኝ የለም ፣ ያጣሁትም የለም።
••
እረኛዬ ሆይ! ካላንተ አባትም እረኛም ጠባቂም የለኝም። አሁንም ስለ ስምህ ጠብቀኝ አሜን!
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

06 Oct, 06:58


ወርኃ ጽጌ - ( ከመስከረም 26 እስከ ኅዳር 6 )
••
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስርአት መሰረት ከመስከረም 26 ቀን እስከ ሕዳር 6 ቀን ያለው 40 ቀን የእመቤታችን ና የልጇን ስደት በማሰብ ወርኃ ጽጌን ( ዘመነ ጽጌን ) ታከብራለች፡፡ ይህ 40 ቀን የእመቤታችንና የጌታ ስደት የሚታሰብበት ዘመን ነው፡፡ ወቅቱ የአበባና የፍሬ ወቅት በመሆኑ እመቤታችን በአበባ ጌታን በፍሬ እየተመሰሉ ጌታችን በአምልላክነት እመቤታችን በፈጣሪ እናትነቷ በተለየ ምስጋና ይመሰገናሉ፡፡
••
በዚህ በወርኃ ጽጌ ( በዘመነ ጽጌ ) የሚጾሙ ክርስቲያኖች ሲኖሩ ጾሙን መንፈሳውያን ሰዎች ሳይታዘዙ በራሳቸው ፈቃድ የሚጾሙት ጾም በመሆኑ ( የፈቃድ ) የትሩፋት ጾም ይባላል፡፡ በቀኖና ቤተክርስቲያን ከታዘዙት ከ7ቱ አጽዋማት ውጪ የሆነ ትርፍ ጾም ማለት ነው፡፡ ከታዘዘው አትርፎ የጾመ ሰው የመጾሙን ዋጋ ያገኛል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ ሥራ የሰራ ሰው ብዙ ክብር እንደሚያገኝ መጽሐፍ ይናገራልና፡፡ ‘’እጅግ ወዳለችና ብዙ ያለው ሐጢአትዋ ተሰርዮላታል፡፡ ጥቂት ግን የሚሰረይለት ጥቂት ይወዳል’’ ( ሉቃ. 7፡47 ) እንዲል፡፡
የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች በክብርም ከእመቤታችን ጋር ይተባበራሉ፡፡ ነገር ግን የጽጌን ጾም የሚጾሙ ሰዎች ለመመጻደቅ መጾም የለባቸውም፡፡ የማይጾሙ ሰዎችንም መንቀፍና መክሰስ የለባቸውም፡፡ የጽጌ ጾም እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ተደርጎ ስላልተወሰነ የማይጾሙ ሰዎች ሕገ ጾምን እንዳፈረሱ አድርጎ መውሰድ ስሕተት ነው፡፡ ይልቁንም የሚጾሙ ሰዎች ቢችሉ መጾማቸው እንዳይታወቅባቸው ቢያደርጉ የተሻለ ነው፡፡ " ስትጾሙ እንደግብዞች አትጠውልጉ " (ማቴ. 6፥16) የተባለው ለዚህ ዓይነቱ ጾም ነው፡፡

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

04 Oct, 09:21


አምላከ ተክለሐይማኖት ማረን
አምላከ ቅዱሳን ታረቀን
ስለቃልኪዳንህ በቁጣ አታጥፋን
••
የአባታችን የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት ጸሎታቸውና አማላጅነታቸው አገራችንን ኢትዮጵያን እና እኛን ህዝቦቿን ከፈተና ይጠብቀን ዘንድ በቃልኪዳናቸው ያስቧት።
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

01 Oct, 14:03


በልዩ መንበሯ ሃገሯ ግሸን ማማሯ
💚💛❤️
እንኳን ለንጽሕተ ንጹሐን ቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ ግሸን ደብረ ከርቤ ዳግማዊት ጎሎጎታ የመስቀሉ መገኛ ታላቅ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
••
በዚህች ዕለትም የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በግሸን ደብረ ከርቤ ማረፉን አስበን በዓሉን እናከብራለን። ቸር አምላክ በኃይለ መስቀሉ ሃገራችንን ከክፉው ሁሉ ይጠብቅልን አሜን!
••
የግሸኗ ማርያም በጦርነት ውስጥ ያሉትን መከራ የከበባቸውን ደጅሽ መርገጥ ያልቻሉትን ልጆችሽን አስቢያቸው አሜን! እኔን የሰማችኝ ወላዲተ አምላክ የእናንተንም ጸሎት፣ ልመናችሁን የልብ መሻታችሁን ሰምታ ለደጇ ታብቃችሁ አሜን!
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችን - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

14 Sep, 08:29


ጨው የሞላብሽ አዲስ ማሰሮ
አለም ጣፈጠ ምሬት ተሽሮ
ተለውጠናል አዲስ ሆነናል
ድንግል ለክብርሽ እጅ ነስተናል
••
አክሊላችን ነሽ ውበታችን
ትምክህታችን ነሽ መፅናኛችን
ስምሽን ጠርተን ከሞት ድነናል
ምልጃሽ እረድቶን ቀና ብለናል
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

11 Sep, 08:37


" እንኳን ከዘመነ ቅዱስ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ቅዱስ ማቴዎስ በሰላም አደረሰን!! "

አዲሱ ዓመት ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር የተሰጠን ሌላ አዲስ እድል ነው። አማኑኤል ከእኛ ጋር ለመሆን የእኛን ሥጋ ተዋሕዷል፣ አምላክነቱ ሳያሳስበው የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አድርጉዋል። በደሃ ቤት አድሯል ፣ በበረት ተወልዷል፣ ከብርድ መከለያ ጨርቅን ፈልጓል ፣ ፍጥረትን የሚመግብ እርሱ ከእናቱ የድንግልናዋን ወተት ለምኖ አልቅሷል ፣ እንደ ሕፃናት በጉልበቱ ድኋል፣ ለእናቱ እየታዘዛት ጥቂት በጥቂት አድጓል። ከአደገም በኋላ ራሱን የሚሰውርበት ጎጆ ሳይኖረው በተራራ ተንከራቷል ፣ ተርቧል ፣ ከኃጢአተኞች በደረሰበት ተቃውሞ ተሰድቧል ፣ ተገፍቷል። ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ሆኗል።

ከእኛ ጋር ለመሆን ብቻ ሳይሆን በእኛ ውስጥ ለመኖር በእለተ አርብ በመስቀል ተሰቅሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ ተሰጥቶናል። እኛስ ወደ እርሱ ሊያቀርበን ይህን ሁሉ ከሆነልን አምላክ ጋር ለመኖር ምን አደረግን? ንስሐ ገባን? ሥጋ ወደሙን ተቀበልን?

ከእግዲህስ በኃጢአት ያረጀ ማንነታችንን እንተው። አዲሱን ዓመት " ማለዳ ማለዳ አዲስ " ከሆነው ፈጣሪያችን ጋር ለመኖር ለራሳችን ብሩህ ተስፋ እንሰንቅ። እስኪ አምና ወድቀን ከተሰበርንበት የዘር ፣ የጥላቻ ጉድጓድ ወጥተን ዘንድሮን ተዋድደን ፣ ተፋቅረን በሰላም እንኑር። እስኪ ደግሞ ወደ ሰላማዊ ኢየሱስ ክርስቶስ ቀርበን ይህችን ዓመት በሰላም ጀምረን እንፈጽማት።

አዲሱ ዓመት የሰላምና  የፍቅር  እግዚአብሔርን  በቅንነት የምናገለግልበት ዓመት እንዲሆንልን እንመኛለን
••
የቲክ ቶክ የገፃችን - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

10 Sep, 08:49


ዮሐንስ ተሽሮ ማቴዎስ ሊሾም ነው።
እንኳን አደረሳችሁ! የአማኑኤል ልጆች
🌼🌼🌼
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

07 Sep, 09:03


❤️ ቅዱስ ሩፋኤል መላዕክት
•••
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ወርኃ ጶግሜን የዓለም ፍጻሜ መታሰቢያ ተደርጋ ትታሰባለች፣ በዚህ የተነሳ ምዕመናን በጾምና በጸሎት (በሱባኤ) ያሳልፏታል፡፡ በተለይም በቅዱስ ሩፋኤል ዕለት ሰማያት የሚከፈቱበት (ርኅዎተ ሰማይ) መሆኑን በማመን ምዕመናን ጸሎታቸውን ከምንግዜውም በበለጠ ያቀርባሉ፡፡ ወደ ወንዞች በመሄድም በሚዘንበው ዝናብ ይጠመቃሉ፡፡ ወርሃ ዿግሜን የጌታችን ምጽአት የሚታሰብበት በመሆኑ የሚዘመረው መዝሙር፣ የሚነበቡ ምንባባትና ቅዱስ ወንጌል እንደዚሁም የሚሰበከው ምስባክ ይህንኑ ምስጢር የሚያሳዩ ናቸው፡፡ በወርሃ ዿግሜን ከሚታሰቡና ከሚከበሩ በዓላት መካከል በየዓመቱ ዿግሜን 3 ቀን የሊቀ መላዕክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አብያተ ክርስቲያናት በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በዓል የሚከበርባቸው ምክንያቶችም ሁለት ናቸው፣ እነርሱም አንደኛው በዓለ ሢመቱን ምክንያት በማድረግ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ቅዳሴ ቤቱ ነው፡፡ ‹ሩፋኤል› የሚለው የስሙ ትርጓሜ ‹ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን፣ የዋህ› ማለት ነው፡፡ ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሩፋኤል ያለ ማቆረጥ ፈጣሪያቸው ልዑል እግዚአብሔርን ከሚያመሰግኑ ቅዱሳን መላዕክት አንዱ ነው፡፡ ‹‹ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ ›› እንዲል (መጽሐፈ ጦቢት)
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

05 Sep, 09:01


መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ
••
መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ከ ሐዲስ ኪዳን አበው አንዱ የሆነ ንፁሓን ነብያት ቅዱስ ገብርኤል እና አባቱ ዘካርያስ ትንቢት የተናገሩለት ከህፃንነቱ ጀምሮ ቅኑዕት እንደ ገበሬ ጽሙድ እንደ በሬ ሆኖ እግዚአብርን ያገለገለ በፍፁም ልቡ አለምን የናቀ ከተድላዋም ከደስታዋም የተለየ አምላክን ለማጥመቅ የታደለ ሐዋርያ ፣ መምህር ፣ ሰማዕት ፣ ባህታዊ ነቢይ ጻድቅ ነው።
••
ቅዱስ ዮሐንስ ረድኤቱ በረከቱ በኛ ላይ
በእውነቱ ይብዛልን ይደርብን አሜን !!
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

03 Sep, 09:11


❤️ አማኑኤል ሆይ!
••
ስፍራ ሳይርቀው የሚረዳ ፣ ዘመን ሳያልፍበት የሚያጽናና ፣ የጠቆረውን ፊት የደስታ ዘይት የሚቀባ ፣ የምህረት አባት ፣ የይቅርታ ጥላ ማን አለ እንደ አማኑኤል በያለንበት ይጠብቀን አሜን!
••
የሚያጽናናኝ የለም እኔ እንዲህ ስከፋ
ህልምም ሆኖብኛል የሰው ሁሉ ተስፋ
ቃልህን የማታጥፈው አንተ ከኔ አትጥፋ /፪/
••
አማኑኤል ሆይ መድኃኒቴ ሆይ
አትተወኝ አንተ ሞትን እንዳላይ /፪/
••••
#አማኑኤል
#photoeditingchallengesstoday
#ortodoncia
#እመቤታችን
#orthodoxchurch
#እግዚአብሔር
#ortodox
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

02 Sep, 08:36


ሞቼ ነበር ተቀብሬ
ጌታ ወደ እኔ ባትመጣ
አንተ ሞቴን ባትሞትልኝ
ወዴት ነበር የእኔ እጣ
ከንቱ ነበር ማንነቴ
ተሽናፊ ለዚች ዓለም
••
ግን አንተ የያዝከው
አባቴ የያዝከው
ይኖራል ዘላለም
••
አኑሮኛል ቸርነትህ ልክ የሌለው ደግነትህ(2)
እንዳንተ አይነት ከዬት ይገኛል
ሁሉም ነገር ትዝ ይለኛል(2)
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

30 Aug, 17:26


ተክለሃይማኖት ባህታዊ
ምድራዊ ሲሉህ ሠማያዊ
በአደባባይ ተተክለሀል
ተክልዬ መልካሙን ፍሬ አፍርተሀል 👏
••
የመነኮሳት መመኪያ ፣ የምእመናን ሁሉ አባት ፣ ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የተሰጡ ሐዲስ ሐዋርያ፣ አጋንንትን የሚያሳዱ ጣዖታትን የሚያርዱ፣ እልፍ አእላፋትን በወንጌል መረብ የሚያጠምዱ፣ በምድር ተወልደው እንደ መልአክ የኖሩ ጻድቁ አባታችን አባ ተክለ ሃይማኖት ያረፉበት እለት ዛሬ ነው። እግዚአብሔር ለወንጌል አገልግሎት የቤታቸውን በር እንደ ተከፈተ ጥለው የወጡትን አባት፣ የገነትን ደጅ ወለል አድርጎ ከፍቶ በታላቅ ክብር የተቀበለበት እለት ነው።
••
እንኳን አደረሳችሁ!
አባ ጸሊ በእንቲአነ!
•••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

30 Aug, 05:37


❤️ የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት  የዕረፍታቸው መታሰቢያ በዓል ነሐሴ 24 ነው
••
አቡነ ተክለ ሃይማኖት የዕረፍታቸው ጊዜ መቃረቡን ባወቁ ጊዜ የመንፈስ ልጆቻቸውን ጠርተው ጌታችን የነገራቸውን ዅሉ አስረድተው አባታዊ ምክርና ተግሣፅ ከሰጧቸው በኋላ ነሐሴ ፳፬ ቀን ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል፡፡
••
የመንፈስ ልጆቻቸውም ለአንድ ቅዱስ አባትና ካህን በሚገባ ሥርዓት በማኅሌት፣ በዝማሬና በምስጋና ቀብረዋቸዋል፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችንና ከቅዱሳን መላእክት ጋር ተገልጾላቸዋል፤ ነፍሳቸውንም ‹‹የጠራሽ፣ ንጽሕት ነፍስ ሆይ ወደ እኔ ነዪ›› ብሎ በክብር ተቀብሏታል፡፡ በመጽሐፈ ገድላቸው እንደ ተጠቀሰው አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዚህ ዓለም የኖሩበት ዕድሜ ዘጠና ዘጠኝ ዓመት ከዐሥር ወር ከዐሥር ቀን ነው።
••
በእናት አባታቸው ቤት ፳፪ ዓመት፤ በከተታ ፫ ዓመት፤ በይፋት ፱ ወር፤ በዳሞት ፲፪ ዓመት፤ በአማራ ፲ ዓመት፤ በሐይቅ ፲ ዓመት፤ በደብረ ዳሞ ፲፪ ዓመት፤ በትግራይና በኢየሩሳሌም ገዳማት ፩ ዓመት፤ ዳዳ በሚባል አገር ፩ ወር፤ በደብረ አስቦ ገዳም ፳፱ ዓመት ከ፲ ቀን መቆየታቸውን መጽሐፈ ገድላቸው ይናገራል (ገ.ተ.ሃ ፶፱፥፲፬-፲፭)፡
•••
የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለ ሐይማኖት ረድኤት በረከታቸው አይለየን
•••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

27 Aug, 08:48


❤️ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
••
በችግር ውስጥ ስከበብ አለው የምትይኝ ፣ ችግሬን ጭንቀቴን የሚሰማ ባጣሁ ጊዜ የውስጤን የምነግርሽ ፣ ዕንባዬን የሚያብስ ፈልጌ ባጣሁ ጊዜ የልቤን ሁሉ የምነግርሽ የማዋይሽ ድንግል እናቴ ሆይ! ጓደኛ ስፈልግ ጓደኛዬ ፣ ዘመድ ስፈልግ ዘመዴ ሁሉ ነገሬ ሆነሽ በመከራዬ ሁሉ ፈጥነሽ የምትደርሺ ባዶ ሆኜ ሳለ ሙሉ የምታደርጊኝ ፣ ሃዘኔን አይተሽ የማትርቂኝ ፣ በጊዜ በሁኔታ የማትቀያየሪ ዘውትር የልቤ አማካሪ
••
የልቤን የማዋይሽ እናቴ ወላዲተ አምላክ ቅድስት ድንግል ማርያም ዘወትር በየጊዜው በየሰዓቱ ማርያም ማርያም ስልሽ ልኖር እመኛለሁና የእኔን የደካማው ባሪያሽ መሻት አንቺን ማመስገን ነውና መሻቴን ፈጽሚልኝ አሜን!
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbinos

❤️ የአማኑኤል ልጆች ❤️

22 Aug, 08:39


ወንጌላዊ ዮሐንስም ከእርሷ በረከትን ተቀብሎ ሰግዶላት ተመልሶ ከሰማይ ወረደ ሐዋርያትን ተሰብስበው ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ ፈጽሞ ሲያዝኑና ሲተክዙ አገኛቸው። እርሱም እንደ አየ እንደ ሰማ ሥጋዋንም በታላቅ ክብር በምስጋና እንደ አሳረጓት ነገራቸው።
••
ሐዋርያትም በሰሙ ጊዜ ዮሐንስ እንዳየና እንደሰማ ባለማየታቸውና ባለመስማታቸው እጅግ አዘኑ። ከዚህም በኋላ እያዘኑ ሳሉ እነሆ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጠላቸውና የፍቅር አንድነት ልጆች ሰላም ይሁንላችሁ ስለ እናቴ ማርያም ሥጋ ለምን ታዝናላችሁ። እነሆ እኔ እርሷን በሥጋ ላሳያችሁ ልባችሁም ደስ ሊለው ይገባዋል አላቸው ይህንንም ብሎ ከእርሳትው ዘንድ ወደ ሰማያት ዐረገ።
••
ሐዋርያትም ዓመት ሙሉ ቆዩ የነሐሴም ወር በባተ ቀን ለሐዋርያት ዮሐንስ እንዲህ አላቸው አምላክን የወለደች የእመቤታችንን ሥጋዋን ለማየት የተዘጋጀን አድርጎ ያሰየን ዘንድ ኑ ይህን ሁለት ሱባዔ በመጾም የክብር ባለቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው በልጅዋ በወዳጅዋ ቀኝ ተቀምጣ አይተን በእርሷ ደስ እንዲለን። በዚያን ጊዜም ዮሐንስ እንዳላቸው በጾም በጸሎት ሱባዔ ያዙ የነሐሴ ወር እንደ ዛሬ ዐሥራ ስድስተኛ ቀን በሆነ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉንም ሐዋርያት ወደ ሰማይ አወጣቸው። በታላቅ ክብር በተወደደ ልጅዋ ቀኝ ተቀምጣ ከሥጋዋ ተዋሕዳ ተነሥታ እመቤታችን ማርያምን አዩዋት። እጆቿንም ዘርግታ የከበሩ ሐዋርያትን እያንዳንዳቸውን ባረከቻቸው በልባቸውም እጅግ ደስ አላቸው።
••
የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም በከበረ ሥጋውና ደሙ ላይ ሠራዒ ካህን ሆነ። እስጢፋኖስም አዘጋጀ ዮሐንስም በመፍራት ቁሙ አለ። ሁሉም ሐዋርያት በመሠዊያው ዙሪያ ቆሙ በዚያን ጊዜ ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ።
••
ጌታችንም የቅዳሴውን ሥርዓት በፈጸመ ጊዜ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው ። ከዚያም በኪሩቤልና በሱራፌል ሠረገላ ተቀምጣ በምታርግ ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ እመቤታችን ማርያምን እንዲህ ብሎ ተናገራት።
••
በዚች ቀን የሆነ የዕርገትሽን መታሰቢያ በዓለም ውስጥ እንዲሰብኩ ልጆችሽ ሐዋርያትን እዘዣቸው። መታሰቢያሽን የሚያደርገውን ሁሉ ተጠብቆም በዚች ቀን ቅዱስ ቁርባንን የሚቀበለውን ኃጢአቱን እደመስስለታለሁ። የእሳትን ሥቃይ ከቶ አያያትም መታሰቢያሽን ለሚያደርግ ሁሉ በዚች ቀን ለድኆች በስምሽ ለሚመጸውት ቸርነቴ ትገናኘዋለች ይህም ሥጋሽ ወደ ሰማይ ያረገበት ነው።
••
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ክብር ይግባውና ጌታችንን እንዲህ አለችው ልጄ ሆይ እነሆ በዐይኖቻቸው አዩ በጆሮቻቸውም ሰሙ በእጆቻቸውም ያዙ ሌሎችም ታላላቅ ደንቆች ሥራዎችን አዩ። እመቤታችንም ይህን ስትናገር ጌታችን ሰላምታ ሰጥቷቸው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረ ዘይት ተመለሱ።
••
የተወደዳችሁ ወንድሞች ሆይ በፍጹም ደስታ መታሰቢያዋን እናደርግ ዘንድ ይገባናል እርሷ ስለእኛ ወደ ተወደደ ልጅዋ ሁልጊዜ ትማልዳለችና።
••
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን። በረከቷም ከርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ከአባ ማትያስ ከሁሉም ሊቃነ ጳጳሳትና ኤጲስቆጶሳት ጋራ ሐዋርያት ከሰበሰቧት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች ከሁላችን ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ነሐሴ)
••••
የቴሌ ግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ - https://t.me/Terbinos
የቲክ ቶክ የገፃችን ይመልከቱ - https://www.tiktok.com/@yeamanuelljochi
የፌስቡኩ ገፃችን ይመልከቱ - https://www.facebook.com/terbino

3,959

subscribers

7,108

photos

883

videos