ሰው በወርቅ ያጌጣል። ዶ/ር አንዱዓለምን ግን ወርቆች ያጌጡበታል። ተመረቀ ከተባለ ወርቅ ከአንገቱ አይታጣም። ገዝቶ ሳይኾን በልጦ አሸንፎ። ጌጥ ሳይኾን ሜዳልያ።
አንድ ወዳጄ ( #Mekbib_Fekede_Argaw ) እንደጻፉልኝ
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላላ ሐኪም ተብሎ ሲመረቅ - የወርቅ ተሸላሚ ነው።
ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በቀድዶ ሕክምና ስፔሻላይዝ አድርጎ ሲመረቅ - የወርቅ ሜዳልያው እርሱን ወደደ።
በሀገራችን ጥቂት ሀኪሞች ብቻ በደረሱበት በጉበት በቆሽት እና ጣፊያ ሰብ ስፔሻላይዜሽን ከዐዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ በህንድ፣ በእንግሊዝ፣ በጀርመን፣ በደቡብ አፍሪካ እና በቱርክ ባካሔደው ጥናት ሰብስፔሻላይዝ አድርጎ ሲመረቅም - ወርቅ ወደ ማጌጫው ገባ።
ሰውዬው ወርቅ ጭንቅላት ያለው ተመራማሪ፣ እጅግ ሲበዛ ትሑት፣ በመንፈሳዊ ሕይወቱ በሥርዓተ ተክሊል ጋብቻውን ፈጽሞ፣ ልጆች ወልዶ፣ በሥጋ ወደሙ ተወስኖ የኖረ ልዩ ሰው ዶ/ር አንዱ ዓለም ዳኜ!
ኧረ እየከፈለ የሚያክምም ነው!
ድሆች ሊታከሙ ከእርሱ ፊት ሲቀርቡ የሚከፍሉት በማጣታቸው ሲብሰከሰኩ እንባቸውን ሲያፈስሱ እንባቸውን አብሶ አይዞዎት እኔ ከፍዬ ይታከማሉ ብሎ ያዝዛል።
+ + + + +
የአማን ይንገስ በለጠ ቅኔ
የመሃይም ብልጠት፤ የፈሪ ሰው በቀል
በሽታን ታቅፎ ፤መድኃኒትን መንቀል።
ሳሙኤል ደባስም እንዲህ ተቀኝተዋል
የታመመች ሀገር የተጎሳቆለች
በሽታዋን አዝላ መድኃኒት ቀበረች!
ዲ/ን ኢ/ር ዓባይነህ ካሤ