ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ @behlateabew Channel on Telegram

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

@behlateabew


የቀድሞ አበው እና እመት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ጥበብ...
👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @behlateabew 👈
👆👆👆👆👆👆👆👆

https://t.me/+RICJUxY54uwNbPXe

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (Amharic)

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አዳዲስ ድምጽ መለያን ከመንፈሳዊ ቦታዎች እንዲተንተን ለሚጠቀሙት ምስጋና መረጃ በነፃነት ለማሰብ ከታላቅ በሽተ ነገርን በሚከተለው ዌብሸይላችን ሻጭና በጣም በጣም በጣም....በተጨማሪም ለማስፋፋት እና መጠቀም ባህር ይኖራል!
ለተጨማሪ መረጃዎች እና መዋጮ ታላቅ በሽተ ነገሮችን ማስፈጸም ወዘተሚስተኪውች @behlateabew በተቃውሞ ሌላሁን እና በመስሪያ ቅንብት ሥራ። በጣም በጣም በጣም! ይህ መረጃ በርኒ እንዲሆን እና እየካፈ አንዷል።nnብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ከሌላውን እና አሁንም በዝርዝር ያነበበችው እትዬ ጸጋ! ከሌላው ግምት እና በአጭር ጊዜ በተጨማሪው ስለ ሁኔታ፣ ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እንዲሆን እና እየካፈ አንዷል!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

17 Feb, 11:42


ጥሩ ነገር ከሆነልህ እግዚአብሔርን አመስግን፥ ያን ጥሩ ነገር ያጸናልሃል፤ መጥፎ ነገር ከሆነብህም እግዚአብሔርን አመስግን፥ ያን ክፉ ነገር ለመልካም ያደርግልሃል፤ ስለ ሁሉም ነገር ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁን!
— ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

13 Feb, 09:28


አቤቱ ሙሉ አርገኝ እኔም ሙሉ እሆናለሁ። አቤቱ አንተ አዋቂ ባለይቅርታ ሐኪም ሆይ፣ ቸርነትህን ባርያህ እሻለሁ፡፡ የነፍሴን ቁስል ፈውስ። በዘለዓለማዊው እቅድህ ያለኝን ቦታ አውቅ ዘንድ የልቡናዬን ዐይን አብራ። ምንም ልቤ እና አእምሮዬ ቢታመሙም ጸጋህ ትፈውሳቸው ዘንድ ፍቀድ።

የሰውን የልቡን ሐሳብ ውስጡንም የምትመረምር ላንተ አቤቱ እኔ ምን እላለሁ? አንተ ነፍሴ ውሃን እንዳጣ ምድረ በዳ አንተን እንደተጠማች ልቤም አንተን እንደምትሻ ታውቃለህ። የአንተ ጸጋ የሚወዱህን ሁል ጊዜ ታድናለች፡፡

ሁልጊዜ ትሰማኛለህና አቤቱ አሁን ከጸሎቴ ፊትህን አታዙር። ልቡናዬ አንተን አዳኟን ከእስራቷ አርነትን ትሰጣት ዘንድ ፍጹም እንደምትፈልግህ ታውቃለህና ፊትህን ከእኔ አታዙር።

አቤቱ መራቤን ታጠግብ ዘንድ መጠማቴንም ታረካ ዘንድ ጸጋህን ወደኔ ላክ፥ ባንተ ያለች መረጋጋትን ፍጹም እሻለሁና።

አቤቱ ጌታዬ ሆይ አንተን የሚወድ እውነትህንም የተጠማ ከቶ መች ጠግቦ ይጠግብሃል? አቤቱ ብርሃንን የምትሰጥ ሆይ ልመናዬን ስማ፥ እንደጸሎቴ ጸጋህን ስጠኝ፥ የፍቅርህ ነበልባል በልቤ ይነድ ዘንድ ከጸጋህ አንዲት ጠብታን በልቤ አኑር። እሳት እሾህና ኮሸሽላን እንደሚያነድ እንዲሁ በልቤ ያለውን ክፉ ሐሳብ የጸጋህ እሳት አቃጥሎ ያጥፋልኝ።

አቤቱ የለመንኩህን ሁሉ አትረፍርፈህ ስጠኝ፥ አምላኬ ነህና ለእኔ ለፍጥረትህ፣ ንጉሴም ነህና ለእኔ ለባርያህ ጸጋህን ፍቀድልኝ። እንደ ቸር አባትነትህም አብዝተህ በጸጋህ ባርከኝ።

ማር ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

12 Feb, 05:42


+• ልብ የሚዘልቁት የቅዱስ ኤፍሬም ድንቅ ጸሎቶች •+

ጸሎቶቻችን ሁሉ በምድራዊ ነገሮች ታጥረው እየተጉተመተሙ ለሚቀሩብን ከንቱ ለምንሆን ለእኛ የትሑቱ ቅዱስ ኤፍሬም ጸሎቶች እጅጉን አስተማሪ ናቸው:: በዚህ ተርጉሜ ያቀረብኳቸው ሁለት ጸሎቶች የሁላችንን ጸሎት ሰማያዊ በሆነው ቅኝት ያስተካክሉልን ዘንድ ተስፋ አደርጋለሁ:: ቅዱስ ኤፍሬም ስለ ምን እንደሚጸልይ ልብ እንበል:: ጸሎቱን እንጸልየው፤ የራሳችንንም ጸሎት እንቃኝበት::

+•ጸሎት አንድ•+

አቤቱ አምላኬ፤ የሕይወቴ ጌታ፤ በስንፍና እና በተመራማሪነት መንፈስ፤ እንዲያውም በመላቅ ምኞት እና በከንቱ ልፍለፋ መንፈስ እንዳልበከል ፈቃድህ ይሁንልኝ::

ከዚህ ይልቅ ለእኔ ለአገልጋይህ የንጽሕና እና የትሕትናን መንፈስ፤ እንዲያውም የትእግስትን እና ባልንጀራን የመውደድን መንፈስ ስጠኝ::

አቤቱ ጌታዬና ንጉሤ ሆይ፤ ለባልንጀሮቼ ክፉ ያለማሰብን እና የራሴን ኃጢአቶች የማየትን ጸጋ ስጠኝ::

አንተ ብጹዕ ነህና፤ ዛሬም ዘወትርም፤ ለዘለዓለሙ አሜን::

+• ጸሎት ሁለት •+

ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የነገሥታት ንጉሥ፣ በሕይወትም ሆነ በሞት ላይ አንተ ኃያል ነህ:: ምስጢር የሆነውንና የተደበቀውን አንተ ታውቃለህ፤ አሳቦቻችንም ሆነ ስሜቶቻችን ከአንተ የተሸሸጉ አይደሉም::

ከምንታዌነት ፈውሰኝ፤ እኔ በአንተ ፊት ክፉ አድርጌያለሁ:: አሁን ሕያው መሆኔ እለት ከእለት ስትቀንስ፤ ኃጢአቶቼ ደግሞ ይጨምራሉ::
አቤቱ ጌታ፣ አምላከ ሥጋ ወነፍስ፣ የሥጋዬንም ሆነ የነፍሴን እጅግ ደካማ መሆን አንተ ታውቃለህ::

አቤቱ ጌታዬ፤ በድካሜ ውስጥ ጉልበትን ስጠኝ፣ በሐዘኔም ውስጥ አጽናኝ:: በቸርነት የላቅህ ጌታ ሆይ፤ አንተ ያደረግህልኝን ማሰብ እንዳልተው አመስጋኝ ነፍስን ስጠኝ:: በደሎቼን ሁሉ ይቅር በለኝ እንጂ ብዙ የሆኑትን ኃጢአቶቼን አታስብብኝ::

አቤቱ ጌታዬ፤ የኔ የክፉውን ኃጢአተኛ ጸሎት አትናቀው:: ከዚህ በፊት እንደጠበቀኝ ሁሉ ለወደፊትም እንዲጠብቀኝ በጸጋህ እስከመጨረሻው አጽናኝ:: ጥበብን ያስተማረኝ ያንተ ጸጋ ነው፤ የእርሷን [የጥበብን] መንገድ የሚከተሉ ብጹዓን ናቸው፤ የክብር አክሊልን ይቀዳጃሉና::

አቤቱ ጌታ ሆይ፤ ምንም የማልረባ ብሆንም ስንኳ አመሰግንሃለሁ፤ አከብርሃለውም፤ ለእኔ ያለህ ምህረት ገደብ የለውምና:: ረዳቴና ጠባቂዬ አንተ ነህ:: የግርማዊነት ስምህ ለዘለዓለም የተመሰገነ ይሁን::

ለአንተ ለአምላካችን ምስጋና ይሁን::

አሜን::

🖋 Fresenbet G.Y Adhanom

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

11 Feb, 09:04


የእግዚአብሔር ቃል ለጠቅላላ ዕውቀት ተብሎ አይጠናም።
ለጠቅላላ ሕይወት ተብሎ ይጠናል እንጂ።
ብዙ ባወቅነ ቁጥር ብዙ የተግባር ሀላፊነት አለብን።
አለማወቅንም የተፈጥሮ ነጻነት ትከለክለናለች።
አእምሮ ለብዎ ያለው ሰው ነጻ የተፈጥሮ ስጦታውን ተጠቅሞ ለነፍስም ለሥጋም የሚጠቀምበትን የተዋሕዶ ዕውቀትን ይቀስማል።
የተማረውን ባይኖረው ግን ሕግ ፈጻሚ ሊባል አይችልም።
በሕገ እግዚአብሔር የሚገኘውን ጸጋም ማግኘት አይችልም።
የእግዚአብሔር ቃል እርሱን በሙምሰል ልምምድ ውስጥ እንድንጓዝ ያስተምረናል።
መልካም ዕውቀት ወደ ሕይወት ይመራል።
መልካም ካልሆነ ግን የማይጠቅም ቃላት ይሆናል።
"አውቄዋለሁ የሚል ትእዛዛቱንም የማይጠብቅ ውሸተኛ ነው እውነትም በእርሱ ውስጥ የለም።ቃሉን ግን የሚጠብቅ ሁሉ በእርሱ የእግዚአብሔር ፍቅር በእውነት ተፈጽሞአል። በእርሱ እንዳለን እናውቃለን።በእርሱ እኖራለሁ የሚል እርሱ እንደ ተመላለሰ ራሱ ደግሞ ሊመላለስ ይገባዋል።" ፩.ዮሐ.፪፥፬-፮ እንዲል።

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

07 Feb, 03:05


እርግጠኛ ነኝ በየትኛውም እምነት ውስጥ ብንሆንም አእምሯችን ይጠይቃል።

መልስ ባለማግኘት የተጨነቃችሁ ወይንም ከጓደኛ ወይ ከቤተሰብ የሚመጣ ጥያቄን ለመመለስ የተቸገራችሁ የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ሊቃውንትን መድቧል።

“ሃሎ መምህር” እንዲመለስልዎ የሚፈልጉትን ኃይማኖታዊ ጥያቄዎች በስልክ ቁጥር 0111 55 32 32 በተጠቀሱት በመደዎል ይጠይቁ፡፡

ለጥያቄዎ ማብራሪያ እና መልስ ከመምህራን ያገኛሉ፡፡

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

01 Feb, 06:12


https://youtu.be/PutTxEm9GP4?si=q3OeIMaCV1W2dK1u

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

29 Jan, 19:16


ደክሜ ባለሁ ጊዜ ከወደቅሁበትም መነሳት ሲከብደኝ ለነፍሳት ርኅሩኅ የሆንሽ ድንግል ሆይ ወደእኔ ነይ። ታማሚው ልጅሽ ከደጅሽ ቆሜ አለሁ፤ ሕመሜን ግን አንቺ ከእኔ በላይ ታውቂዋለሽ፥ ባለመድኅኒቱም ልጅሽ ነው።

ድንግል ሆይ "ልትድን ትወዳለህን?" እባክሽ አትበይኝ። መታመሜን የማላውቅ ጎስቋላ በሽታዬን የምመርጥ ሞኝ ነኝና። በሲቃ ነፍሴ ወደአንቺ ትጣራለች፥ ወደልጇ ይዘሻት እንድትወጪ ዐይን ዐይንሽን ታይሻለች።

ንጹሕ ለሆንሽ ለአንቺ የማቀርበው የሚመጥን እጅ መንሻ ከእኔ ዘንድ የለኝም፥ ለአዳም ዘር ስጦታ ሆነሽ በእግዚአብሔር ለተሰጠሽ ለአንቺ ከቶ ምን ማቅረብ እችላለሁ? ስለዚህም ድንግል ሆይ እንደምታስፈልጊኝ አውቀሽ ሕይወትን ለሚሞላ ልጅሽ "ብርታት አልቆበታልና ና ወደእርሱ ዘንድ እንሂድ" በይው፣ የቸሩ እረኛ ደግ እናት ሆይ ተኩላዎች ከልጅሽ በጎች እንዳይለዩኝ ወደእኔ ነይ፣ በመንገድ ወድቄ እንዳልቀር የደጉ ሳምራዊ እናት ሆይ ባለመድኅኒት ልጅሽን ይዘሽ ወደእኔ ነይ፣ ጉድፍ የሌለብሽ መሶበወርቅ ሆይ ተርቤያለሁና የሕይወት ሕብስት ልጅሽን ታቅፈሽ የነፍሴን ረሀብ ታስታግሺልኝ ዘንድ ነይ፣ የምግባር እንስራዬ ባዶ ነውና ከምንጭ ዳር እጠብቅሻለሁ ጥምን የሚያጠፋ የሕይወት ውሃ ልጅሽን ይዘሽ ነይ፣ መንገድ ጠፍቶኝ እጠብቅሻለሁ መንገድ እና ሕይወት እውነትም የሆነውን ልጅሽን ይዘሽ ወደእኔ ነይ፥ ብርታት አጥቻለሁና እኔ እስክመጣ አትጠብቂኝ ሰላማዊቷ ርግብ ሆይ አንቺ ቀድመሽ ወደእኔ ነይ።

@ዲያቆን እስጢፋኖስ ግርማ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

28 Jan, 15:46


“ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ”
ትርጉሙ "ሞት ለማናኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል፡፡"
ቅዱስ ያሬድ
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሠላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን።
መልካም በዓል ይሁንልን!!!!!!!!!!!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

24 Jan, 08:58


"ሌቦች ወርቅና ብር ያለውን እንጂ ድርቆሽና ገለባ እንዲሁም ሰንበሌጥ ያለውን ቤት አይበረብሩም። ዲያብሎስም የሚያጠቃው (የሚፈትነው) መንፈሳዊ ምግባራትን የሚያበዙትን ሰዎች ነው።"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

21 Jan, 04:47


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ዘንድ በአሁኑ "አሐቲ ቤተከርስቲያን" አለን ? "በአሁኑ ሰዓት ቅዳሴ ከአለ በሥጋ ወደሙ"።

ይድረስ ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባቶች ና ሰባኪያን

የከተማ ለአንድ ክብረ በዓል ለdecoration ብቻ በሚሊዮኖች ብር ይመደባሉ። ገጠር በአገልጋይ ፣ በጧዋፍ እና ዕጣን ዕጥረት ዓመት ሙሉ ያለአገልግሎት ዘመኑን አሻግረሉ።

ልክ ጌታችን ሐሙስ ማታ ከሰዱቃውያን እና ከፈሪሳውያን ፈተና በፊት ወደ ጌቴሴማኒ ሄዶ ብቻውን እንደ ቆመ ሁሉ የገጠር አቢያተ ክርስቲያናት ባለፉት ዓመታት በትልቅ እና ውስብስብ ፈተና ውስጥ ወድቀው፣ የድኅነት በሮች ተዘግተው፣ ከአውደ ምህረቷ በትምህረቷ ልጆቿን ስትሰበስብበት የነበሩ አደባባዮቿ ዛሬ የከብቶች ግጦሽ ሆነው የቀሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ ቅዳሴና ማህሌትን መሳተፍ ሳይሆን ሰምተው ለመደሰት እንኳን በናፍቆት ሲጠባበቁ የነበሩ ምዕመናን ተስፋ ወደ መቁረጥ ተቃርበዋል፡፡ ተስፋም ጨልሞአል።

በዓመታዊ ክብረ በዓላትና በጥምቀት እንኳንስ ከመንበሩ ወጥቶ ህዝቡን ባርኮ የማያውቁ፣ ቅዳሴና የውስጥ አገልግሎት የማያገኙ ታቦታት እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ በሥጋ ተወልደው በመንፈስ ግን በጥምቀት ከእግዚአብሔር ያልተወለዱ፣ ክርስቲያኖች ሆነዉ የድኅነት በራቸው ተዘግታባቸው ንስሃ አባት አግኝተው ከኃጥያታቸው ተፈትተው የንስሃ ሕይዎት እንኳን እንዳይኖሩ እናታቸው በተ ክርስቲያን የአገልግሎት መካን ሆናባቸዋለች፡፡

ከዓመታዊ ክብረ በዓል እንኳን በአገልጋዮች ችግር ምክንያት ታቦት ከመንበሩ ተነስቶ ሳይወጣ ቀርቶ፣ የቤተ ክርስቲያን፣ም ደጅ ተዘግቶ ማየት ምን ያህል ልብ ያደማ ይሆን? መንፈሳዊ አገልግሎትን ለማግኘት መናፈቃቸውስ እስከ መቼ ይሆን? ማንስ ይድረስላቸው? ቅዱስ ጳውሎስ " እኛ ሁላችን ወንድማማች ነን፡፡ አንድ ህብስትም ተካፍለናል፡፡

በአንድነትም ክርስቶስን እንመገባለን፡፡" ያለውንስ አስበን እኛ ለምን በወንድማማችነታችን አልደረስንላቸውም?
የከተማ አድባራትና ካቴድራሎች ከ10 ያላነሱ ሰባኪያነ ወንጌል አሏቸው፡፡ የገጠር አጥቢያዎች ግን እንደ ወረዳ አንድ እንኳን ሰባኬ ወንጌል የሌላቸው፣ የከተማ አድባራት የአንድ ሰባኪ ደመወዝ በወር እስከ 20ሺህ ሲሆን የአንድ ገጥር አጥቢያ ዓመታዊ በጀት ግን 8ሺህ የማይሆን፣ መሪጌቶችና ሊቃውነት በከተማ በአንድ አጥቢያ ከ20 እስከ 100 ሲሆኑ በገጠር ግን እንደ ወረዳ አንድ እንኳን በሌለበት እንድ ሐዋርያት በጸሎት ሃይማኖት "ሐዋርያት በሰበሰቧት በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን፡፡" ስንጸልይ እንዴት አውነት ሊሆንልን ይችላል?

የከተማ አቢያተ ክርስቲያናት ብዙ ሊቃውንት፣ ሰባኪያነ ወንጌል እንዲሁም በርካታ የሚያስተምሩ አባቶችን ይዘው አውደ ምህረታቸው ሁሌም በወንጌል፣ የውስጥ አገልግሎትም፡- በማህሌት፣ በሰዓታት፣ በኪዳን፣ በቅኔ፣ በቅዳሴ አሸብርቆ በገጠር ያሉ ወንድሞቻቸው ደግሞ ይህን ሁሉ አገልግሎት አጥተው በነፍስም በስጋም ተርበው ሳሉ ነገ ጌታ ሲመጣ " ተርቤ ኣላበላችሁኝም፣ ተጠምቼ አላጠጣችሁኝም" ብሎ ሲጠይቀን ምን ብለን እንመስለት?
ታርዤ አላለበሳችሁኝም ለሚለውም ጥያቄ የገጠር ምዕመናን ቤተ ክርሰቲያነቸው ተዘግቶባቸው በጥምቀት ክርስቶስን ሳናለብሳቸው ቀርተን ምን አይነት መልስ እንሰጥ የሆን?

የሰማያዊው ህብስት እና የሕይወት ውኃ ምንጭ የሆነው የክርስቶስ እናትና ሙሽራ ቤተ ክርስቲያን ተዘግታ ከማየት የሚበልጥ ምን ኀዘን አለ? አንድ ሰው ለምድራዊው ሀገሩና ወገኑ ተቆርቁሮ አክቲቪስት እንደሚሆን ገንዘቡንና ያለውን ነገር ለዚህ ጉዳይ እንደሚያውል ሁሉ ለሰማያውያን ወይም መንፈሳውያን ወንድሞቹስ ለምን አይቆረቀርም? አባቶቻችን፣ ወንድሞቻችን፣ እናቶቻች፣ እህቶቻችን፣ ጓደኞቻችን እና ልጆቻችን በችግር ውስጥ እያሉ እኔ ክስርቲያን ነኝ ለማለትስ ምን ሞራል ይኖረናል? ክርስቶስ ዳግም ተመልሶ ሲመጣ ለምታልፈው ዓለም ሌትና ቀን እየደከምክ፣ የሐብትና የደም መስዋዕትነት እየከፈልክ ለማታልፈው ለሰማያዊ ርስትህ ለቤተ ክርስቲያንህስ እጅህ ወዴት ነው? መችስ ጊዜ ይኖርሃል? ሀብትህስ የት አለ? ሁሉን ለሰጠህ ለመስጠት የተከፈተ የልብ የስቶታ በር አለህን? ወላጅ እናትህ፣ አሳዳጊህ በአገልግሎት የወላድ መካን ስትሆን ምን ይሰማህ ይሆን?
ስጋዊ ቤትህ ጸድቶ የሕይዎት እንጀራ ቤት የጌታ ቅዱስ ስጋና ክቡር ደም የሚፈተትባት መንፈሳዊ ቤትህ የገጠሯ ቤተ ክርስቲያን በመካነ መቃብር ተከባ እንዲህ መስላ የቅዳሴ እና የሌሎች አገልግሎት ድምጽ ጠፍቶት የአሞራዎች ድምጽ ከቧት ያየ አይንና የሰማ ጆሮ ምን ይበል?

የምዕመናን የመዝሙራቸው ድምጽ ሲስተጋባባት የነበረች የቤተ ከርስቲያን ደጅ በአራዊት እና በእንስሳት ፈርሳ ክርስቲያኖች በችግራቸው ጊዜ እረፍት የሚያገኙባት የነበረች ቀን የከብቶች እና የሌሎች እንስሳት ማረፊ ሌሊት የአራዊት መዝናኝ ሆና ስናገኛት ሂሊናችን ምን ያህል ይረበሽ? ጌታ ታምሜ አልጠየቃችሁኝም እንዳለው ከስጋና ከነፍስ መከራ መፍትሄ ለማግኘት ወደሷ የመጡት እልፍ ክርስቲያኖች ተዘግታ ሲያገኟት በሀዘን ላይ ሀዘን ተጨምሮባቸው ውስጣቸው ቆስሎ የሚያጽናናቸውንም አጥተው የሰላም በር በሆነችው በቤተ ክርስቲያን ፊት ቆመው ሲያለቅሱ ከማየት በላይ እንባ ለምን ይውረድ?
ደዌ ስጋ ታመው በየሆስፒታሉና በየፀበል ስፍራዎች ከወደቁት በላይ አገልግሎት በማጣት የተዘጋችውን ቤተ ክርሰቲያን አይተው በመንፈሳዊ ቅናት የታመሙትን ማን ይጠይቃቸው? ድውያነ ስጋን ገንዘብና ምግብ ይዘን እንጠይቃቸዋለን፡፡ አገልግሎት በማጣት ታመው ዐይናቸው በእንባ የልባቸው ሀሳብ ስለ ቤተቨ ክርስቲያን በማሰብ የታመሙትን በምን እንጠይቃቸው የሆን? ትናንት ዳዊትና ጽና ይዘው ቤተ ክርስቲያንን በዜማ ሲያገለግሉ ቆይተው በእርጅና ምክንያት በቤት የቀሩት አባቶች በእርጅና ድካም ላይ የቤተ ክርስቲያናቸውን መዘጋት ሲያዩ ይህን ከማየት ይልቅ ሞትን አይመርጡምን?

ትላንት መጾረ መስቀልን ይዘው ተንስዑ ሲሉ የነበሩ ዲያቆናት ዛሬ እጃቸው ባዶ ቀርቶ በልባቸው ስለ ቤተ ክርስቲያናቸው እያንጎራጎሩ ሲሄዱ የማን ጆሮ ሰምቶ አለንላችሁ ይበላቸው? እናቶችና አባቶች በእርጅና ዘመናቸው ንስሃ ገብተው ከክርስቶስ ጋራ መኖር እየተመኙ ምኞታቸው ሳይሳካ ቀርቶ ሌሊት መንጣፋቸውን በእንባ የሚረጥቡትን፣ በተዘጋችው ቤት ክርስቲያን ደጅም እንባቸውን እየፈሰሱ እንደ ራሄል ወደ ሰማይ የሚረጩትን ማን አይቶ እኔ ደረስኩላችሁ ይበላቸው?

ግን ለምን ክርስቲያን በመንፈሳዊ ወንድሙ ላይ ልቡ ጨከነ? አንዲት ቤተ ክርስቲያን አለችን የሚል ወገንስ ለወገኑ አለሁልህ የሚል ድምጹ ለምን ጠፋ? ይህ ትውልድ ሌላው እንኳን ቢቀር አለሁልህ ብሎ አእምሮውን የሚያረጋጋለትን ሰው ይፈልጋል፡፡ ከዚህ በኋላ ቤተ ክርስያኔ ተዘጋች ብሎ አካሉና ሀሳቡን ለዓለም አሳልፎ የሰጠውን ትውልድ ማን ከተኩላ መካከል ይመልሰው? ማንስ በኀዘን የተሰበረውንና የፈረሰውን የቤተ ክርስቲያን ህንፃ ቀና ያድርገው? ሕዝቅ 22 እንደ ተባለው በፈረሰው በኩል ለመጠገን ዪቆመው ማነው? በመንፈሳቸው ታመው ወድቀው የቆሰሉትን መንፈሳዊ ወገኖቹን ዘይት ቀብቶ ደግፎ የሚያነሳ ደጉ ሳምራዊ ማነው? እንደ ሐዋርያው ፊሊጶስ ባልንጀራውን በበጎ የሚያስበው የት አለ?

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

21 Jan, 04:47


ጌታችን ይቺ ከሁሉ አብልጣ ሰጠች ብሎ እነዳመሰገናት ጊዜውን፣ እውቀቱን፣ ጉልበቱን ገንዘቡን፣ ሙያውን በመስጠት ጌታውን ለማስደሰት የተዘጋጀ ማነው? የክርስቶስ አካል የሆነችዋ ቤተ ክርስቲያን ልጆቼ ድረሱልኝ ብላ አሰምታ ስትጣራ ድምቷን ሰምቶ እናቴ አለሁልስ የሚላት እውነተኛ ልጇ የመስቀሉ ስር ዮሐንስ ታዲያ ማነው?

የምድር አቀማመጥ እና በሁሉም የፈተና ሰይፍ እየተወረወረባት ልጆቿን ለማትረፍ የምትቾኸዋን የገጠር ቤተ ክርስቲያን ማን እኔ አለሁልሽ ይበላት? በአቡነ ተክሃይማኖት ለይ ሲወረወር የነበረው የፈተና ሰይፍ በመንፈሳዊ የሀይማኖት አገልግሎት ደካሞች የሆኑትን የገጠር ክርስቲያኖችን ምን ያህል ያቆስላቸው ይሆን? የተክልዬ አምላክ ድረስልን! የሀይማኖት ጽናትን እንዲሰጠን ተክልዬ በአምላክህ ፊት ቁምልን እያሉ እጃቸውን ወደ እግዚአብሔር ለሚዘረጉት የቱ መንድም አለሁላችሁ ይበላቸው?
ስነ ልቦናቸው የተሰበረውን ካህናትና አገልጋዮችንስ ማን የጠግናቸው? ለፈርሰው ህንፃ አብያተክርስቲያናት ደግሞም ኃጢአትን በማብዛት በቁም ለሞቱት ህንፃ ሥላሴ የሆኑት የሰው ልጆች እንደ ዲያቆን ፊሊጶስ በቅልጥፍና አስተምሮ አጥምቆ በደስታ ለመመለስ ለመንፈስ ቅዱስ ምርጥ እቃ ለመሆን የተዘጋጀ ማነው? እውነተኛ ፌቨን በመሆን ለክርስቲያን ወገን የምትስብ ሴት ማናት? የተራበውን ሕዝብ ጌታ አበርክቶ እንዲመግባቸው ሁለት አሳና አምስት እንጀራን ወደ ጌታ የሚያቀርቡ እነማን ይሁን ?

የአባቶች አይን በእንባ ብዛት ፈዞ ብሌናቸው ፈዟል፡፡ ከንፈሮቻቸውም ድረሱልን በማለት እየጮሁ እና እየወተወቱ ደረቀ፡፡ በመከራው ጊዜ ርዝመት ምክንያትም አንገታቸው ተሰብሮ አቀረቀሩ፡፡ አንጀታቸው በምጥ እንደ ተያዘች ሴት ተረጋግቶ አልቀመጥ በሏቸዋል፡፡

ነቢዩ ኢሳያስ በትንቢቱ ስለ ድንግል ማርያም ሲናገር እግዚአብሔር ዘርን ባያስቀርልን ኖሮ እንደ ሰዶም በሆንን ገሞራንም በመሰልን ነበር እንዳለው አወሷም ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል እንዳለችው የተባረከ ዘር በመሆን በተለያየ መልኩ በዘመናዊ ፈተና ተጠላልፎ ለፍርድ እሳት ተላልፎ እየተሰጠ ያለውን ትውልድ ከዚህ በኋላ ደርሶለት ከጥፋት የሚያድነው የተመረጠ ትውልድ ማነው? እንደ ዘሩባቤል መቅደሱን መልሶ በማነጽ እስራኤላቅያን ዘነፍስን ከጥፋት የሚታደግ ሰው ከወዴት እንጥራ? እንደ ነሂሚያ የፈረሰውን የእየሩሳሌምን ግምብ እና ቅጥር መልሶ ለመሥራት ከገኖቹ ጋር አንድ ልብ በመሆን ወደ ሥራ የሚገባ ከወዴጥ እናምጣ?
ጌታችን ያቺ አመንዝራ የነበረች ሴት ዋጋው ውድ የሆነ ጥሩ መዓዛ ያለው የከበረ ሽቱ ይዛ እሱ ወዳለበት ወደ ስምዖን ቤት ስትሄድ ሌሎቹ ሲነቅፏት ከመሞቴ በፊት ለቀብሬ አዘጋጅታኛለችና ተዉአት እርሷ ያደረገች ይህ ነገር ይህ የመንግስት ወንጌል በሚሰበክበት ቦታ ሁሉ እሷ ያደረገች ዳግሞ ለመተሰቢያ ይሆንላት ዘንድ ይነገርላታል እንዳለው ምንም እንኳን ሰውነታችን በኃጥያት ቢቆሽሽም መልካም መዓዛ ያለው ሽቱ በመያዝ የክርስቶስ አካል ወደ ሆነችው ቅድስት ቤተ ክርሰቲያን ማን ይሂድ? በስጋ ከዚህ ዓለም ሳንሰናበት ምን አይነት በጎ ነገር ሠርተን በእግዚአብሔር ፊት ለመታሰቢያ ይሁንልን?

ሞቼ ከዚህ ዓለም ላይ ከማለፌ በፊት ለነገዋ ቤተ ክርስቲያኔ አገልግሎቷ እንዲሰፋ ምን ይዤ ልቅረብ? ምን ሠርቼም በመንፈስ የወለደችኝን መንፈሳዊ እናቴን ቤተ ክርስቲያንነን ላስደስት?

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

20 Jan, 09:23


ካህን ለተጋቢዎች ከሚጸልየው ጸሎትና ከሚሰጣቸው ቡራኬ ውስጥ አንዱ እንዲህ ይላል፦

"በቃና ዘገሊላ ሰርግ የወረደች የእግዚአብሔር በረከት ትደርባችሁ። በመካከላችሁም ስምምነትን ታድርግላችሁ፤ ፍቅርን በልቡናችሁ ታሳድርባችሁ፤ ብዕላችሁን ያብዛላችሁ፤ ቤታችሁን ያንጽላችሁ፤ ረጅም ዕድሜ ጸጥ ያለ ኑሮ ይስጣችሁ፤ የተባረኩ ልጆችንም ይስጣችሁ። አሜን!"

ከገ/እግዚአብሔር ኪደ ፌስቡክ ገጽ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

19 Jan, 16:48


❝ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ በመጠመቁ ምክንያት ጥምቀትን በእርሱ ጥምቀት ባርኮ ሰጠን። ክርስቶስ የተጠመቀበት የዮርዳኖስ ወንዝ መለኮታዊውን ብርሃን ለበሰ። በእርሱ ጥምቀት ወንዞች ፣ ጅረቶች ፣ ምንጮች ፣ ሁሉ ተቀደሱ። ... መድኅናችን ሆይ በአንተ ጥምቀት የውኃ ምንጮች ሁሉ ተቀደሱ ፤ ስለዚህም ውኃ የመንፈሳውያን ልጆች መገኛ ማኅፀን ሆነች። ❞
ቅዱስ ኤፍሬም

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

18 Jan, 08:33


✟"ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጠመቁ ምክንያት ከብሉይ ወደ ሐዲስ፥ ከኦሪት ወደ ወንጌል አሻገረን፤ የመንግሥተ ሰማያትን ደጅ ከፈተልን፤ ወደ ሀገራችን (ወደ ሰማይ) ይጠራን ዘንድ ብቻ ሳይኾን ሊነገር በማይችል ክብር ያከብረን ዘንድም ቅዱስ መንፈሱን ላከልን፡፡"

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ።
❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖❖
መልካም በዓል!!!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

16 Jan, 06:37


በገና መግዛት የሚትፈልጉ
#በነጻ_transport_ያሉበት_ቦታ_እናደርሳለን

👉ለማዘዝ
🤳09-29-18-24-65 or @Akiya_mart

https://t.me/+D6VnZzXYklFiODc0

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

16 Jan, 04:25


የጥምቀት ገሃድ እና ሰንበት

✥እንደ ሥርዐተ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ ማንኛውም ክርስቲያን ሊጾማቸው
የሚገቡ የአዋጅ አጽዋማት 7 ናቸው፡፡ እነዚህም ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ሐዋርያት፣ ጾመ ፍልሰታ፣ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ገሃድ፣ ጾመ ነነዌ እና ጾመ ድኅነት (የዓርብና ረቡዕ ጾም) ናቸው፡፡ የገሃድ ጾም ከ7ቱ የአዋጅ አጽዋማት አንዱ ነው ማለት
ነው፡፡
✥ገሃድ ማለት “ለውጥ፣ ልዋጭ” ማለት ነው፡፡ … ወይም እንደ ዘይቤው “ግልጥ”ማለት ነው፤ “ይፋ” ማለት ነው፡፡ የአምላካችን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መገለጥን የምናስብበት ስለሆነ ገሃድ ይለዋል
በተጨማሪም ዕለቱን
ፍትሐ ነገስት ጾመ ድራር እያለም ይጠራዋል

✥ልደትና ጥምቀት ረቡዕና ዓርብ
ሲውሉ በሌሊት ስለሚቀደስና ስለሚበላ በለውጡ በዋዜማው ሐሙስና ማክሰኞ
ይጾማል፤በሌላም ቀን ቢውል የጥምቀት ዋዜማ ቅዳሴው ለሊት ስለሆነ ይጾማል ይህም ጾም በያመቱ እንዲጾም በቀኖና ቤተክርስቲያን ተወስኗል፡፡

✥ነገር ግን የዘንድሮን 2017 ዓ.ም ለየት የሚያደርገው ጥር 10ቀን ቅዳሜ ሰንበት ላይ ስለዋለ የምንጾመው ከጥሉላት (ከፍስግ) ምግቦች ብቻ ይሆንና አርብን እስከ 12 ሰአት እንጾማለን ማለት ነው
ከብርሃነ ጥምቀቱ በረከትን ያድለን
በዓሉን የሰላም በዓል ያድርግልን አሜን

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

14 Jan, 07:13


“ወዳጄ ሆይ! የትዕቢት መርዝ ተጠራቅሞ አብጦብሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡ የስግብግብነት ትኩሳት አስቸግሮሃልን? ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ደግነትንም ትማራለህ፡፡ የምቀኝነት ብርድ አስቸግሮሃልን? እንኪያስ ወደ ሰማያዊው መዓድ ቅረብ፤ ምህረት ማድረግንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ ትዕግሥትን የማጣት እከክ ይዞሃልን? እንኪያስ ወደ ቅዱስ ሥጋዉና ክቡር ደሙ ቅረብ፤ ራስን መግዛትንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ልል ዘሊል ብትሆን ይህን መንፈሳዊ መዓድ ተመገብና ብርቱ ትሆናለህ፡፡ ቆሽሸሃልን? እንኪያስ ወደዚሁ መብልና መጠጥ ቅረብ ብዬ እመክርሃለሁ፤ ንጽሕናንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡”

ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

14 Jan, 05:10


"አቤቱ አንተን ደስ ከማያሰኝ ሐሳብ እንለይ ዘንድ መለየቱን ስጠን....አቤቱ የእውቀት ዓይኖችን ስጠን፤ ዘውትር አንተን ያዩ ዘንድ ፤ጆሮቻችንም ያንተን ብቻ ቃል ይሰሙ ዘንድ።"

ቅዳሴ እግዚእ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

13 Jan, 05:58


"መብላትና መጠጣት ብቻውን ጓደኝነት አይስብለውም፣እንዲህ ዓይነቱ ጓደኝነትማ ዘራፊዎች እና ነፍሰ ገዳዮች እንኳ አላቸው። ነገር ግን ወዳጆች ከሆንን፣ እርስ በርሳችን ከልብ የምንተሳሰብ ከሆነ፣ እርስ በርሳችን በመንፈሳዊነት የምንረዳዳ፣ ጓደኞቻችንን ወደ ገሃነም የሚወስዱ እንቅፋት አናድርገው።
      ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

11 Jan, 16:05


ጌታችንንና መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወደው የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ በሁለት ወገን ድንግል ከምትሆን ከቅድስት ማርያም መወለዱንም የማያምን ሰው ሁሉ እንግዳ እስከሚሆን ምጽአቱ ድርስ ጳውሎስ እንደ ተናገረ የተለየ ይሁን፡፡
        ሥርዓተ ቅዳሴ
          @behlateabew

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

11 Jan, 16:03


በእውነት ለሰው ወገን አማላጅ የምትሆኝ አምላክን የወለድሽ ንጽሕት ቅድስት ድንግል ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ፡፡
      ሥርዓተ ቅዳሴ
           @behlateabew

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

10 Jan, 05:08


እሰይ ነጋ!ቀኑን ሙሉ ክፋትን በመስራት አንተን ስናሳዝን እንዳንውል ጠብቀን::

ከራሳችን ጠብቀን
ከክፉ ሐሳቦቻችን ጠብቀን
ከጠላት ወጥመድ ጠብቀን
እረኛችን ሆይ ጠብቀን

መልካም ቀን

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

08 Jan, 18:22


"ለመወለዱ ጥንት በሌለዉ አስቀድሞ ዓለም ሳይፈጠር በመለኮቱ ከአብ በተወለደ ዳግመኛም እኛን ለማዳን ቡሃላ ዘመን ከቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በእግዚአብሔር ልጅ እናምናለን ።የቀኑ ቀጠሮ ሲደርስ እግዚአብሔር ልጁን ላከ ከድንግልም ተወለደ።"
ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

08 Jan, 09:07


"ከዛሬ ጀምሮ ስላምን እንከተላት ክርስቶስ በዚህች ዕለት ተወልዷልና።"
ቅዱስ ያሬድ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

06 Jan, 05:30


ከአብ የተወለደ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሚሆን የእግዚአብሔር ቃል ሰው ሆነ በመለኮቱ መዋረድ ሳይኖርበት በፈቃዱ ተዋርዶ የተገዥ ባሕርይን ተዋሐደ።

ሰው ሆይ ሥጋ ያልነበረው እርሱ ለአንተ ብሎ ሥጋን ተዋሐደ፤ ሰው ሆይ በመለኮቱ አይዳሠሥ የነበረ ነፍስን ሥጋን የተዋሐደ ቃል ለአንተ ብሎ ተዳሠሠ፤ በመለኮቱ ጥንት የሌለው እርሱ ጥንት ያለውን ፍጹም ሥጋ ተዋሐደ።

አይታይ የነበረው የሚታይ ሥጋን ተዋሐደ፤ የማይለወጥ እርሱ በሚለወጥ ሥጋ ተዳሠሠ፤ የማይለወጥም አደረገው።

ባዕል እርሱ ከሌዊ ወገን በተወለደች በድንግል ማኅፀን አደረ፤ ሰማይን በደመና የሚሸፍን እርሱ በጨርቅ ተጠቀለ፤ የነገሥታት ንጉሥ በበረት ተጣለ።


ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ አጢፎስ
ምዕራፍ ፰

👉 @behlateabew 👈

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

06 Jan, 05:20


"በቀዳማዊት ሔዋን አለመታዘዝ ምክንያት ሞት በሰው ላይ ሰለጠነ፤ በዳግማዊት ሔዋን (ድንግል ማርያም) መታዘዝ ምክንያት ሕይወት ወደ ዓለም መጣ፡፡ ሞት ኃይሉን አጣ፡፡"
ቅዱስ ሄሬንዮስ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

06 Jan, 04:39


"ድንግል ፈጣሪዋን ወለደችው፤
እርሱም እናቱን ፈጠረ፤
የፈጠረውንም ሥጋ መልሶ ተዋሐደው።"
ቅዱስ ኤፍሬም

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

05 Jan, 08:42


“ከእግዚአብሔር አብ በተወለደው በቀዳማዊ ልደቱ የእግዚአብሔር አብ ልጅ ነው፤ ከድንግል በተወለደው በደኃራዊ ልደቱ የሰው ልጅ ሆነ፡፡ እርሱ አንዱ በመለኮት ከአብ ጋር አንድ የሚሆን የሚተካከል ፍጹም አምላክ ነው፤ እርሱ ብቻ ከድንግል በተወለደው ልደት በሥጋ ከሰው ጋር አንድ የሚሆን ፍጹም ሰው ነው፡፡”
ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ናጣሊስ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

05 Jan, 08:28


 “ይህች ቤተልሔም መንግሥተ ሰማያትን መሰለች”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

05 Jan, 08:19


“በጨለማና በሞት ጥላ ውስጥ ለሚኖሩ ሰዎች ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው፤ በቅዱሳን የሚያድር እግዚአብሔር እኛን ለማዳን ልዩ ከሆነች ድንግል ሰዉ ሆኗልና ኑ ይህን ድንቅ እዩ፣ ስለተገለጠልን ምስጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋህዷልና ቅድምና የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት”
ቅዱስ ኤፍሬም

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

23 Dec, 17:08


"ድንግል ማርያም የሽቱ መኖሪያና የሕይወት ውሃ ምንጭ ናት የማኅፀንዋ ፍሬ ሰውን ሁሉ አድንዋልና። ከእኛም እርግማንን አጠፋልን። "
ቅዱስ ኤፍሬም

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

21 Dec, 09:43


“በከየት ወለሀወት ገዳምከ፤
ምድረ ዋልድባ ቅድስት ሰሚዓ ዜና ሞትከ... “

እንኳን ለአባታችን አባ ሳሙኤል የእረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

17 Dec, 08:32


አኀዊነ በኵሉ አስተፋጠንኩ ከመ እጽሐፍ ለክሙ በእንተ ሕይወተ ኵልነ እስመ ጥቀ እጽሕፍ ለክሙ ጽሑቀ ወአስተበቍዐክሙ ከመ ትትቀነይዋ ለእንተ ተውህበት ለቅዱሳን ሃይማኖት።| ወንድሞቻችን ስለ ሁላችን ሕይወት አጽፍላችሁ ዘንድ በሁሉ ቸኰልኩ እንድጽፍላችሁ አጅግ ጓጕቼ ነበርና ለቅዱሳን የተሰጠችውንም ሃይማኖት እንድ ታገለግሏት እማልዳችኋለሁ ።
የይሁዳ መልክት 1-3

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

15 Dec, 17:16


ወምንተ ይበቁዖ ለሰብእ ለእመ ኩሎ ዓለመ ረብሐ ወነፍሶ ኃጉለ (ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?)” (ማቴ. 16:24 )

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

14 Dec, 05:41


ኢሰማዕነ ወኢርኢነ ወኢነገሩነ አበዊነ ከመቦ ባዕድ አምላክ ዘእንበሌከ

| ከአንተ ሌላ (ከአንተ በቀር ሌላ) አምላክ እንደ አለ አልሰማንም አላየንም አባቶቻችንም አልነገሩንም ።
መፅሐፈ ሰዓታት

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

14 Dec, 03:02


“የክርስቶስ ፍቅር እንደምናውቀው እና እንደምንጠብቀው “እንደሆነው የሚቀበል(accept as who they are)” አይነት ሳይሆን የክርስቶስ ፍቅር ሰዎችን እንደሆኑት የሚቀበል እና ‘አዲስ፣ዋጋ የሚታጣለት፣ታላቅ’ አድርጎ የሚለውጥ ነው።”

አበምኔት አይሪኒ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

12 Dec, 05:12


“ጸቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍርኪ፤ ሀሊበ ወመዓር እምታሕተ ልሳንኪ፤ወይቤላ ንዒ ንሑር ኀበ ደብረ ከርቤ ውስተ አውግረ ስሂን"
ቅዱስ ያሬድ

እንኳን አደረሳችሁ
በዓታ ለማርያም

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

05 Dec, 07:21


ወዘእንበለ ንስአሎ ይሁብ ፍትወተነ|ሳንለምነው የምንሻውን ይሰጠናል::
ኪዳን ዘነግህ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

04 Dec, 11:58


የመድኃኒት ብልቃጥ ድንግል ሆይ ጸሎቴ በልጅሽ ፊት የተወደደ ይሁን የሙሴ መሥዋዕት በምድረ በዳ የአሮን መሥዋዕት በምስክሩ ድንኳን የተወደደ እንደ ሆነ፡፡
አርጋኖ ዘረቡዕ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

03 Dec, 08:36


ባዘንኩም በተቆረቆርሁ ጊዜ የኃዘኔ መፅናኛ ነሽ። ባለቀስኩም ጊዜ የለቅሶዬ መተዊያ ነሽ። በዘመርሁ ጊዜ ለእጄ እንደ መሰንቆ ለጣቶቼም እንደበገና ነሽ። በተራብሁ ጊዜ ለሆዴ ትመግቢኛለሽ በተጠማሁ ጊዜ እኔን ለማርካት የሕይወት ውሃን የተመላሽ ነሽ። በተጨነቅሁ ጊዜ ጭንቀቴን ታርቂያለሽ። በቆሰልኩም ጊዜ ቁስሌን ታጠጊያለሽ። በበደልኩም ጊዜ ኃጢያቴን ታቀልያለሽ። በርኩሰቴም ጊዜ ንጹሕ ታደርጊኛለሽ። የደኸየሁም ጊዜ ለድህነቴ ባለጸግነት ሀብቴ ነሽ።
አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

30 Nov, 05:47


ማርያም ጽዮን ታቦተ ቃለ ጽድቅ መንፈቀ ዕሥራ፣ ዕጐላት እምዕጐሊሆን ከመ ኪያኪ አፍቀራ፣ አፍቀርኩኪ አፍቅርኒ እምይእዜ ለግሙራ

➥|እውነተኛው የእግዚአብሔር ቃል (ዐሠርቱ ቃላት) የተጻፉብሽ የሙሴ ታቦት (ጽላት) ነሽ፡፡ (ጊደሮች) ርግቦች ከልጆቻቸው ይልቅ አንቺን እንደወደዱ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ፈጽሜ አፈቅርሻለሁና ረድኤትሽ አይለየኝ፡፡

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

26 Nov, 04:03


የይሁዳ መሳም ውጤቱ ጌታን አሳልፎ መስጠት ነው። የለንጊኖስ መውጋት ውጤቱ ልጅነት የምናገኝበትን ማየ ገቦ ማስገኘት ነው። እንዲህ ከሆነ ከይሁዳ ሰላምታ የለንጊኖስ መውጋት ይሻላል።

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

23 Nov, 04:34


“አንጨነቅ ይህን በማድረጋችን የምናተርፈው ምንም ነገር የለምና። ከልክ በላይ በማሰብ ራሳችንን ነው የምናሰቃየው አሰብነውም አላሰብነውም እግዚአብሔር ይሰጣል! እንዲያውም አብዛኛውን ጊዜ ሳንጨነቅ።ስለዚህ በመጨነቅ ምን እናገኛለን ራሳችንን ከመቅጣት ውጪ?”

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ድርሳን 6

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

22 Nov, 07:37


እምኵሉ ምግባረ እኩይ አድኀና ለነፍስየ፤
ነፍሴን ከክፉ ሥራ ሁሉ አድናት፤

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

21 Nov, 11:47


"መልአከ ሰላምነ ሊቀ መላእክት ሚካኤል ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ አዕርግ ጸሎተነ ቅድመ መንበሩ ለንጉሥ ዐቢይ"

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

20 Nov, 22:15


ረዳኤ ምንዱባን ሚካኤል ረዳኤ ምንዱባን በከመ ከመ ታለምድ ዘልፈ🙏

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

15 Nov, 05:21


እመቤቴ አንቺስ ከስደት ወደ ሀገርሽ ናዝሬት ተመለሽ። የአኛስ ልብ ከአመፃና ከእርኩሰት ስደት መች ይሆን የሚመለሰው ?
አብርሂ አብርሂ ናዝሬት ሀገሩ
ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መፆሩ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

15 Nov, 05:19


ሀገረኪ ገሊላ እትዊ እስከ መቼ ድረስ እመቤቴ በሰው ሀገር ትኖሪያለሽ ? ሀገርሽ ገሊላ ግቢ። እናቴ ሆይ ወደ ልቤ ግቢ የእኔም ልብ ወደ ልጅሽ ወደ ወዳጅሽ ሚጠት መመለስን ይፈልጋልና ።

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

31 Oct, 11:48


"እኔ እለምናለሁ አቺ ጸሎቴን ታሳርጊያለሽ ልጅሽም ኃጢአቴን ያስተሠርያል። የልቤን ግዳጅ ይሰጠኛል። እኔ ቁስለኛ ነኝ አቺ የመድኃኒት ሙዳይ ነሽ። ልጅሽም ባለ መድኃኒት ነው፡፡"
አርጋኖ፣ ዘሐሙስ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

31 Oct, 06:37


"ቤተክርስቲያንን የሚያስቀጥሉ ሦስት ሰንሰለቶች አሉ እነርሱም:---
ትዳር ፣ ምንኩስና እና ክህነት ናቸው።

እነዚህ እክል ስለገጠማቸው ነው ቤተክርስቲያን እየተቸገረች ያለቸው እንጂ ሌሎች ሰዎች ወይም አህዛብ ክፉ ስለሆኑ አይደለም። እነሱ ደግ የሚሆኑበት ዘመን ነገም እኔ አልጠብቅም ሰይጣን ባለበት መልካም ነገር አይመጣም።

እኛ ግን የጎደለን ይህ ነው፣ በተከበረ ትዳር ፣በተከበረ ምንኩስና እና በተከበረ ክህነት ቤተክርስቲያን ትቀጥላለች።

ምሳሌ እንዴት ካልን፦
የተከበረ ትዳር:- የተከበረ መነኩሴ ይወልዳል።
የተከበረ መነኩሴ:- የተከበረን ጵጵስናን ያመጣል።
የተከበረ ጳጳስ:- የተከበረን ክህነትን ይሾምና
የተከበረው ክህነት:- የተከበረ ትዳርን ባርኮ ያጋባል። የተከበረው ትዳር መልሶ እንደገና የተከበረ ካህንን ይወልዳል።

በዚህ ዑደት ነው ቤተክርስቲያን ተጠብቃ የምትኖረው። አሁን ግን ምንጩ ደፍርሷል። ለዚህም ሁላችንም መስተካከል አለብን። አሁን እኔ ሁሉም ሥርዓት እየፈረሰ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ! ተምረን ማግባትና፣ተምረን መመንኮስም ሆነ ክህነት መያዝን ማስቀጠል አለብን።"

ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

30 Oct, 16:24


ነገ ረቡዕ በጥናታዊ ጽሑፍ መድረክ ከቻሉ ይሳተፉ።

-ርዕስ- Mystical Theology: Insights from Spirituality -ምሥጢራዊ ነገረ መለኮት ከኦርቶዶክሳዊ መንፈሳዊነት እይታ አንጻር''

-ነገ ረቡዕ ጥቅምት 20 /02/2017 ዓ.ም

-ሰዓት 11:00

-አቅራቢ አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ(ፕ/ር)

-ቦታ 4 ኪሎ ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

23 Oct, 07:48


የጌቴሴማኒ እናቶቻችንን ጥያቄ መመለስ የክብር ጉዳይ ነው
CBE 1000003777689
--
ገዳሙን የተሳላሚ ያህል አውቀዋለሁ፡፡ የሰው ፊት ማየት አይወዱም፡፡ አንድ ገዳም እንዴት መኖርና ማኖር እንዳለበት ብሔራዊ ማሳያ ናቸው፡፡ ይሠራሉ፡፡ ያስተምራሉ፡፡ ያሳድጋሉ፡፡ ይጦራሉ፡፡ በልመና አይታዩም፡፡ የሠሩትን ሲሸጡ ብቻ አይተናል፡፡ አሁንም ፊታችን የቆሙት የነበረውን ለማስቀጠል እንጅ ልመናን የማይቋረጥ ዘላቂ ተግባር አድርገው አይደለም፡፡ አንዳንድ ጊዜ … ያልታሰበ ቀን የሰው ፊት ያቆማል፡፡ እናቶቻችን ሰው ፊት መቆም አልለመዱም፡፡ ጊዜ ጥሏቸው እንጅ ኩሩዎች ሠርቶ አዳሪዎች ነበሩ፣ ናቸው፡፡ በነበሩበት የመንፈስ ልዕልና እንዲቀጥሉ ማስቻል የክብር ጉዳይ ነው፡፡ የሽግግር ጊዜያቸውን አሳጥረን በነበሩበት የትሩፋት ተግባር ማስቀጠል ግዴታችን ነው፡፡

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

22 Oct, 13:24


"መጥፎ ቀን እና ጥሩ ቀን የሚባል ነገር የለም። ያለው ጸሎት አድርገህ የወጣህበት ቀን እና ጸሎት ሳታደርግ የወጣህበት ቀን ነው። ያልጸለይክባቸው ቀናት በክፉ ምኞትና የሥጋ ፍላጎት የተሞሉ ስለሆኑ ክፉ ቀናት ናቸው።"
— ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

19 Oct, 16:52


"እግዚአብሔር አምላክ የለመኑትን አይነሳምና ሁላችሁም ስለ ሀገር ሰላም፣ስለ ቤተክርስቲያን አንድነት፣ስለ ሕዝብ ደህንነትና አብሮነት ጸልዩ፤"

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

17 Oct, 18:23


አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይመክራሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይናገራሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይፈፅማሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይሠራሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያስማማሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያከናውናሉ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይልካሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያሰለጥናሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ምስክር ይሆናሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ሰውን ይስባሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያለምዳሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይመክራሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያነጻሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያጸራሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያከብራሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያጸናሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያስጨክናሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያስተምራሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይጋርዳሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያለብሳሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ባለምዋል ያደርጋሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይቀመጣሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይፈርዳሉ ።
አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይመረምራሉ ።
እንዲህ እናምናለን እንዲህም እንታመናለን አንድነትን ሳንለይ የተለየ እንዳይሆን ። የተቀላቀለ እንዳይሆን እንለይ።

እንደ አብርሃምና እንደ ይስሐቅ እንደ ያዕቆብም ሦስት የምንል አይደለም በገጽ ሦስት ሲሆን አንድ ነው እንጂ ።
ከፍጥረት ሁሉ እንደሚቀድም እንደ አዳም አንድ የምንል አይደለም በባሕርዪው አንድ ሲሆን ሦስት ነው እንላለን እንጂ ።

ክፉዎች አይሁድ ባለማወቃቸው የእግዚአብሔርን ገጽና አካል አንድ ነው የሚሉ በደለኞችን የይስማኤል ወገኖችንም እነሆ እንሰማቸዋለን ልቦናቸውን ያሳወሩ ናቸው ።

አምላኮቻቸውም ብዙ አጋንንቶቻቸው ብዙ የሆኑ በጣዖት የሚያመልኩ አረማውያንን እነሆ እናያቸዋለን ። እኛ ግን በጎ ጐዳና የሚያስተምሩትን እንከተላለን ። ሐዋርያት እንዲህ እያሉ እንዳስተማሩን ።

አብ ፀሐይ ነው ወልድ ፀሐይ ነው መንፈስ ቅዱስም ፀሐይ ነው ። ከሁሉ በላይ የሚሆን አንድ የእውነት ፀሐይ ነው ።

አብ እሳት ነው ወልድ እሳት ነው መንፈስ ቅዱስም እሳት ነው ። በልዕልና ያለ አንድ የሕይወት እሳት ነው ።
አብ ጎሕ ነው ወልድ ጎሕ ነው መንፈስ ቅዱስም ጎሕ ነው ። በብርሃኑ ፀዳል ጨለማ የራቀበት አንድ የጧት ጎሕ ነው ።

አብ ጒንደ ወይን ነው ወልድ ጒንደ ወይን ነው መንፈስ ቅዱስም ጒንደ ወይን ነው ። ዓለሙ ሁሉ የጣፈጠበት አንድ የሕይወት ወይን ነው ።

አብ ሐሊብ ነው ወልድ ሐሊብ ነው መንፈስ ቅዱስም ሐሊብ ነው ። ጭማሪ የሌለበት አንድ ሐሊብ እርሱ ነው ።

እንዲህም እናምናለን እንዲህም እንታመናለን ።

ምንጭ: – ቅዳሴ ማርያም

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

15 Oct, 18:39


አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ!

አንድን የሥጋ ቁስል ለመፈወስ ለእያንዳንዱ ሰው ከባድ ነው፤ የነፍስን ቁስል መፈወስ ግን ለኹሉም ቀላል ነው፡፡ የሥጋ ቁስል ለመፈወስ መድኃኒት ብሎም ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነፍስን ለመፈወስ ግን ቀላል ብሎም ወጪን የማይጠይቅ ነው፡፡ ሥጋን ከዚያ ከሚያሰቃይ ቁስሉ ለመፈወስ አድካሚ ነው፡፡ ምክንያቱም በቀዶ ጥገና ምላጭ መቀደድ አለበት፤ መራራ መድኃኒቶችም ሊጨመሩበት ይገባል፡፡ ነፍስን ለመፈወስ ግን እንዲህ ዓይነት ነገር አያስፈልግም፡፡ ፈቃደኛ መኾን ብቻ በቂ ነው፤ ፍላጎቱ ካለ ኹሉንም ነገር ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ የእግዚአብሔር መግቦቱም እስከ አሁን ድረስ ይህ ነው፡፡ ሥጋ ቢቆስል ያን ያህል ከባድ ጉዳትን አያመጣብንም፤ ምክንያቱም ምንም ባንታመምም እንኳን ሞት መጥቶ ይህን ሥጋችን ያፈርሷል፤ ያበሰብሷልምና፡፡ ነፍሳችን ብትታመም ግን ጉዳቱ ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሔር የነፍስን ሕመም ለመፈወስ መድኃኒቱ ቀላል፣ ምንም ወጪና ስቃይ የሌለበት ያደረገውም ስለዚሁ ነው፡፡ ታዲያ ምንም እንኳን በሕመሙ ምክንያት የሚያገኘን ጉዳት ያን ያህል ብዙ ባይኾንም የገንዘብ ወጪን የሚጠይቀው፣ ሐኪም የሚያስፈልገው፣ ብዙ ስቃይ ያለበት ሥጋችን ሲታመም እርሱን ለማከም እጅግ የምንደክም ኾነን ሳለ፥ እጅግ ብዙ ጉዳት የሚያመጣውን፣ እርሱን ለመፈወስ ወጪ የማይጠይቀውን፣ ለማስታመም ሌሎች ሰዎች የማያስቸግረውን፣ እንደ ምላጩና እንደ መራራ መድኃኒቱ ስቃይ የሌለበትን ይልቁንም ከእነዚህ አንዱስ እንኳን ሳይፈልግ በእኛ ኃይል ባሉ ምርጫና ፈቃድ ብቻ መዳን የሚችለውን፣ ይህን ማድረግ ሳንችል ስንቀርም ከባድ ፍርድና ቅጣት ስቃይም እንደሚያገኘን በእርግጥ እያወቅን የነፍሳችንን ቁስል ችላ የምንል ከኾነ ሊደረግልን የሚችል ምሕረት እንደ ምን ያለ ምሕረት ነው? እኮ የምናገኘው ይቅርታ እንደ ምን ያለ ይቅርታ ነው?

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
          በእንተ ሐውልታት መጽሐፍ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

13 Oct, 13:36


https://www.youtube.com/watch?v=1ns_y9-wQDs

1000631459793

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

13 Oct, 07:21


“እርሱም የአካሉ ማለት የቤተ ክርስቲያን ራስ ነው፤”
(ቆላ. 1፥18)
***
ነገረ ቅዱሳን በትክክል ለመረዳት ነገረ ክርስቶስን ርቱዕ በሆነ መንገድ መረዳት ይገባል። ራሱ የተበላሸ ከሆነ ግን አካሉ ሁሉ የተበላሸ ይሆናል። (አረዳዱን ነው።)
አዲስ ኪዳን በአብዛኛው ስለ ክርስቶስ የሚናገር ሆኖ ሳለ ስለ ድንግል ማርያም እና ሌሎች ቅዱሳን 'ከተባለው በላይ' ለምን ታስተምራላችሁ? የሚል ትችት በተደጋጋሚ እንሰማለን። በርግጥም ወንጌል ዋናው መልእክቱ ስለ ክርስቶስ ማንነት፣ የማዳን ግብራት እና ትምህርት ነው። ነገር ግን ከጥቅስ ቆጠራ ባለፈ ወደዚህ የወንጌል ትምህርት መንፈስ ጠልቀን ስንገባ ክርስቶስን ከሞተላት፣ ከተዋሐዳት እና ሕያው ትምህርቱን ከሰጣት ከቤተ ክርስቲያን ለመለየት መሞከር መቀነስ (reductionism) ነው። መቀነስም ብቻ ሳይሆን ማዛባት ነው። የቅዱስ ጳውሎስን ስለ ክርስቶስ እና ቤተ ክርስቲያን መዋሐድ ጥቅስ ሳይመርጥ የሚመረምር ክርስቶስ ከቤተ ክርስቲያኑ (ከቅዱሳኑ ኅብረት) ጋር ያለውን ምሥጢራዊ ተሳትፎ ሊያቃልል አይችልም። የቅዱስ ጳውሎስ ተወዳጅ የቅድስና አንቀጽ "በክርስቶስ ውስጥ (in Christ) ሆናችሁ" የምትል ናት። (ሮሜ. 6፥3፣ 8፥1፣ 8፥39፣ 12፥5፤ 1ኛ ቆሮ 1፥13፣ 1፥30፣ 4፥10፣ 12፥12፣ 15፥22፣ 16፥24፤ 2ኛ ቆሮ. 1፥21፣ 2፥14፣ 5፥17፤ ገላ. 2፥20፣ ወ.ዘ.ተ...)
ወደ ወንጌል ጠልቀህ ግባ፤ የክርስቶስና የቤተ ክርስቲያኑ ዘርፈ ብዙ አንድነት ግልጽ ይሆንልሃል። ክርስቶስን የበለጠ ለማወቅ በሞከርሽ መጠን ከቅዱሳኑ ጋር ያለውን ጥልቅ የፍቅር አንድነት አለማየት ስህተት ይሆናል።
ይህም ይታወቅ ዘንድ ከጥንት ጀምሮ ቅዱስ ሄረኔዎስን በመሳሰሉ አበው ሲብራራ የነበረው የነገረ ማርያም ጉዳይ በእጅጉ ጎልቶ የወጣው ታላቁ የተዋሕዶ ነገረ ክርስቶሳዊ ጉዳይ ከመ*ናፍ*ቃን ለመጠበቅ ተጋድሎ በነበረበት በ5ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱስ ቄርሎስ ዘመን ነው።
የወንጌል ማዕከል የሆነው የቁርባን ምሥጢር የግድ ወደ ነገረ ቅዱሳን ይወስዳል፤ የክርስቶስና የቤተ ክርስቲያኑ የአንድነት ምሥጢር ነውና። (ማቴ. 26፥26፣ ዮሐ 6፣ 1ኛ ቆሮ. 11)
#Dn_Bereket_Azmeraw

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

12 Oct, 05:59


የምንጸልየው እግዚአብሔር ምን ማድረግ እንዳለበት ለመንገር ሳይሆን እግዚአብሔር ምን ማድረግ እንዳለብን እንዲነግረን ነው።
        ቅዱስ አውግስጢኖስ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

12 Oct, 04:42


"የሐዋርያት ጉባኤ ስለሆነች ስለአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም እንማልዳለን።"
መጽሐፈ ሚስጢር

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

09 Oct, 18:34


“አንድ ምንም እውቀቱና ልምዱ የሌለው ሰው ዝም ብሎ መሬት ስለ ቆፈረ ብቻ ወርቅ አያገኝም፡፡ ከዚያ ይልቅ ምንም ረብሕና ጥቅም የሌለውን ድካም ያተርፋል እንጂ፡፡ ባስ ካለም የቆፈረው ጉድጓድ ተደርምሶበት ሕይወቱን ሊያጣ ይችላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት እንደሚነበብና እንዴት መረዳት እንዳለበት ያለወቀ ሰውም ይህን ሰው ይመስላል፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ  አፈወርቅ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

07 Oct, 11:32


Channaloota barumsa Amantaa Ortoodoksii Afaan Oromoottiin itti baranuu.

በአፋን ኦሮሞ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ትምህርቶችን የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና ብሒላተ አበው  ወይም የአበውን ምክር ለመከታተል እነዚህ Channels  ይቀላቀሉ።

Ortoodoksii Ishee Dhugaa
(እውነተኛይቷ ኦርቶዶክስ )
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
👉 @Ortodoksiidhugaa 👈
👉 @Ortodoksiidhugaa 👈


https://t.me/+UE8OsP4gdv93PxwT

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

07 Oct, 08:07


የዓለም ሁሉ መድኃኒት የምትሆን ብላቴና እግሯ የተመላለሰበቱን ምድር እስም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ ይቅርታን የምታሰጥ ብላቴና ጥላዋ ይነካኝ ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡ የብርሃን ልጅ ወደ ሄደችበት እከተላት ዘንድ ማን በከፈለኝ የእግሯንም ጫማ እሸከም ዘንድ ማን በከፈለኝ፡፡

መጽሐፈ አርጋኖን - ዘሰኑይ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

06 Oct, 06:37


🌕🌖🌗እንኳን #ለወርኃ_ጽጌ በሰላም በጤና አደረሰን አደረሳችሁ!🌓🌔🌕

በሀገራችን የመስከረምና የጥቅምት ወራት የአበባ ወራት /ዘመነ ጽጌ/ ናቸው፡፡
ይህም ወቅት ተራሮች በአበባ የሚያጌጡበትና ለዓይን ማራኪ የሚሆኑበት ጊዜ ነው፡፡

በዚህም ዘመን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ......

✟...... “ስለልብስስ ስለምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴት እንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፡፡ አይደክሙም፣አይፈትሉም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም፡፡ እግዚአብሔርን ዛሬያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህየሚያለብሰው ከሆነ እናንተ እምነት የጐደላችሁ እናንተንማይልቁን እንዴት እንግዲህ ምን እንበላለን ምንስ እንጠጣለን?ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ ..."....✟
/ማቴ.5፡28-33/

በማለት የተናገረውን ቃል በማሰብ መጨነቅ የሚገባንመንግሥተ ሰማያት ለመግባት እንጂ በዚህ ዓለም ስላለው ነገር እንዳልሆነ፤ ተራሮችን በአበባ ያለበሰ አምላክ በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረንን እኛን ለኑሮ የሚያስፈልገንን ምግብና ልብስ እንደማይነሳን እያሰብን የምንዘክርበት ወቅት ነው፡፡

እንዲሁም ክቡር ዳዊት
👉 ✟.....«ተዘከር እግዚኦ ከመ መሬት ንሕነሰብእሰ ከመ ሳዕር መዋዕሊሁ ወከመ ጽጌ ገዳም ከማሁ ይፈሪ፤አቤቱ እኛ አፈር እንደሆን አስብ ሰውስ ዘመኑ እንደሣር ነውእንደ ዱር አበባ እንዲሁ ያብባል ነፋስ በነፈሰበት ጊዜያልፋልና».....✟
መዝ.1ዐ2፤14-16


በማለት እንደ ተናገረው የሰውሕይወት በሣር ይመሰላል፡፡ ሣር አድጐ አብቦ ከዚያ በኋላይደርቅና በነፋስ አማካኝነት ያ የረገፈው ሣር እየተነሣየነበረበት ቦታ ስንኳ እስከማይታወቅ ድረስ ይሆናል፡፡

ሰውም ከአደገ በኋላ በሕማም ፀሐይነት ይደርቅና በሞተ ነፋስነት ይወሰዳል፡፡ ከዚያ በኋላ ወደ መቃብር ሲወርድ የነበረበት ቦታ ይዘነጋል፡፡

#ስለዚህ_ዘመነ_ጽጌ_ሰው_ዘመኑ_እንደ_አበባ_በቶሎ_የሚረግፍ_መሆኑን_በማሰብ_ይህ_ዘመን_ሳያልፍ_መልካም_ሥራ_ለመሥራት_ትንሣኤ_ኅሊና_የሚነሣበት_ጊዜ_ነው፡፡

ቅዱስ ያሬድ ለዘመነ ጽጌ የሠራው ድጓም ይህንኑ የሰውን ዘመን አጭርነት የሕይወቱን ኢምንትነት በዚህ ሕላዌ የተፈጠረ ሰው በዚህ ዓለም ክፉ ሥራ መሥራት እንደሌለበት ሁልጊዜ
#በተዘክሮተ_ሞት_እንዲኖር የሚያስረዳ ነው፡፡

✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥✥
ሁላችንም በመቅረብ እንድናውቅና ማኅሌተ ጽጌ በመጸለይና ማኅሌቱን በመቆም በመጾም የእመቤታችንን በረከትና ረድኤት የልጇን የክርስቶስን ምሕረት ለማግኘት ያድለን!

✥ እመ አምላክ ድንግል ማርያም በረድኤቷና በበረከቷ አትለየን!


በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ
ከሐመር መፅሄት የተወሰደ፣ መስከረም 25 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

05 Oct, 11:28


ማኅሌተ ጽጌ

ተአምርኪ ማርያም ተሰብከ በኦሪት
አመ ተሰነዓውኪ ጳጦስ ምስለ መለኮት
ዘርእየኪ ሙሴ ሊቀ ነቢያት
ጸልልኒ በአዕፁቅኪ ሐመልማላዊት ዕፀት
ሦከ ኃጢአትየ ያውዒ ጽጌኪ እሳት፡፡

-ትርጉም- “ማርያም ሆይ ነበልባል ከሐመልማል ተዋሕዶ ሙሴ በደብረ ኮሬብ ባየ ጊዜ ተአምርሽ በኦሪት ተሰበከ ተነገረ፡ ፡ ምሳሌሽ በሐመልማልና በእሳት አምሳል የታየ ማርያም ሆይ ጽጌ ልጅሽ ኃጢአቴን ያጠፋልኝ ዘንድ በጥላሽ ሥር አስጠጊኝ፡፡” (አንድ ሊቅ እንደተረጎሙት)

እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

05 Oct, 09:22


https://youtu.be/z2zAd762nv4?si=qSbzRG1OrDq-sMQf

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

01 Oct, 03:59


"እኔ በስምሽ አምናለሁ፥ አንቺም ስለእኔ ትማልጃለሽ፥ ልጅሽም ስለአንቺ የልመናዬን ዋጋ ይሰጠኛል።"
— ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

30 Sep, 11:23


https://youtu.be/L0skZvJ1_w4?si=9JnpmdmHzhMgZg29

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

30 Sep, 10:16


የእመቤታችን ወዳጆች!
እንኳን ለብዙኃን ማርያም በዓል አደረሳችሁ!

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

28 Sep, 07:33


"የሰው ዘር በሙሉ ኃጢአት፣ እጅግ ሰፊ ከሆነው ከእግዚአብሔር ምሕረት ጋር ሲነጻጸር፣ ውቅያኖስ ውስጥ የተበተነ አንድ እጅ አፈርን ይመስላል::"
ማር ይስሐቅ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

27 Sep, 17:38


"እነሆ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ በእግዚአብሔር ማመንም ተመልሷል፤ እውነትም [ወንጌልም] ወደ ዓለም ኹሉ ደርሷል፡፡ ቅዱስ መስቀሉ ተገልጧል፤ ሰማዕታትም [ከመስቀል በኋላ ሞት ሞት መኾኑ እንደ ቀረና የሹመት የሽልማት ማሳ መኾኑን ዐውቀው አብረው] ተገልጠዋል፤ በክርስቶስ ማመንም በኹሉም ዘንድ ተሰራጭቷል፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

26 Sep, 09:51


✞´ መስቀል ኃይላችን ነው !
✞´ ኃይላችን መስቀል ነው !
✞´ የሚያፀናን መስቀል ነው!
✞´ መስቀል ቤዛችን ነው !
✞´ መስቀል የነፍሳችን መዳኛ ነው !
✞´አይሁድ ይክዱታል እኛ ግን እናምነዋለን!
✞´ ያመነውም እኛ በመስቀሉ እንድናለን፣ ድነናልም።
          የዘወትር ጸሎት
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን🙏
መልካም በዓል

ብሒላተ አበው ወእመት ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ

26 Sep, 09:49


"በመስቀል ላይ ሲነግሥም በፈቃዱ ነው፡፡ በመስቀል ላይ መከራውንም አላፈራም በፈቃዱ ዓለሙን ያዳነበት ፈቃዱም የተገለጠበት ነውና፡፡ የተሰቃየውም አስቀድመን እንደተናገረነው እሩቅ ብእሲ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ሥጋ ለብሶ በለበሰው ሥጋ ነው እንጂ፡፡"
        ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም
     ⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️
💠  @behlateabew  💠
💠  @behlateabew  💠
    ⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️⛪️

10,019

subscribers

1,780

photos

16

videos