ስለ ስራ! @selesera Channel on Telegram

ስለ ስራ!

@selesera


ስራ በእውቀት እንዲሰራ እንተጋለን!
FB - https://www.facebook.com/groups/1153093882014917/?ref=share&mibextid=NSMWBT
Youtube - https://www.youtube.com/@SilSira-zs5rw
Tiktok - tiktok.com/@sile.sira
WhatsApp - https://whatsapp.com/channel/0029Va5Ch0O9WtBw5eGcdZ3H

ስለ ስራ! (Amharic)

ስምኛነት እና አስተማሪነትን በመሆን የስራ ቦታ እንዴት እንደሚገኝ እንችላለን? 'ስለ ስራ!' በላይ በቦታ እና እንዲሰራ ያለንን ሽንፊል ቦታ ማስገኛ እና እንዴት እንደሚቀርብ እንግዲህ ተደርጎ እንገናኘዋለን። በፈረስ ቅንብሙ በመተማመን ቦታዎችን ይመልከቱ ታስብፋለ። የFacebook, Youtube, Tiktok, እና WhatsApp እቅድም እየሆነ ምንም ምልክቶች አልተለመነም ፡፡ ስለሚሰጥ በአጭሩም መረጃዎ ቦታን በመለዋወጥ የምልክቶችን ማግኘት ለስራ ቦታ ይጠቅሱ። ስራ እስከ ወራት እንዳሉ መስሪያ ማንኪያ ራስ ንድፊን መርምርን እና ኡቡዪትን አስፍፏል ፡፡

ስለ ስራ!

16 Feb, 02:25


ከዶ/ር ቢላል ጋር አስደሳች ቆይታ ነበረን!
.
በርካታ አድማጮች በታደሙበት የቴሌግራም ቻናላችን የቀጥታ ስርጭት ስራ ፈጣሪዎች ሊኖራቸው ስለሚገባ የልቦና ውቅር ዶ/ር ቢላል ሰፋ ያለ ማብራሪ ከተጨባጭ ምሳሌዎች ጋር አቅርቦልናል። በጥያቄና መልስ ሰአታችንም ከበርካታ አድማጮች ለቀረቡለት ጥያቄዎች አርኪ ምላሾችን በማቅረብ በርእሳችን እንዲሁም ተያያዥ ነጥቦች ላይ ጥልቅ ግንዛቤ እንዲኖረን ረድቶናል። እንግዳችንን በስለ ስራ አባላት ስም እያመሰገንን የውይይታችን የድምፅ ቅጂ በቅርብ የሚለቀቅ መሆኑን እናሳውቃለን!

የእንግዳችን አድራሻ
Bilcor, adot cinema 4th floor, 0979963535

.
@everyone

ስለ ስራ!

15 Feb, 19:48


Live stream finished (2 hours)

ስለ ስራ!

15 Feb, 18:21


እንደምን አመሻችሁ ተከታታዮቻችን  . . .

ውይይታችን ተጀምሯል!

ውይይቱን ማስታወሻ በመያዝ በጥሞና እና በአንክሮ እንድትከታተሉ  እንጋብዛለን።

ከርዕሱ ጋር የሚዛመዱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ከስር ባለው ኮሜንት መስጫ ሳጥን ላይ ማስፈር ትችላላችሁ! 👇👇👇

የውይይቱን ሊንክ ለሌሎች ጋብዙ!
https://t.me/selesera?livestream

ስለ ስራ!

15 Feb, 17:41


Live stream started

ስለ ስራ!

15 Feb, 17:40


Live stream scheduled for

ስለ ስራ!

15 Feb, 14:26


ቀኑ ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 8 ማታ 2:45 ላይ ነው ☺️

ስለስራ ፈጠራ በብዙ አጋጣሚዎች እንሰማለን። ስለስራ ፈጣሪዎች ልዩ ባህሪያት፣ ስለአላማ ሰውነታቸው፣ ለብዙዎች ስራ ስለመፍጠራቸው፣ የማህበረሰብን ችግር ስለመፍታታቸው፣ ወዘተ...

እነዚህ ስራ ፈጣሪዎች በምን አይነት መንገድ እያሰቡ እዚህ ስኬት ላይ እንደደረሱ ማወቅ አያጓጓም?

ይህን የስኬታማ ግለሰቦች ባህሪያት ምንድናቸው የሚለውን ለማስተማርና ጥያቄዎቻችሁን ለመመለስ በዛሬው የውይይት መሶናዶዋችን ላይ ወንድማችን ዶ/ር ቢላል ሽኩር መሀከላችን ይገኛል።

📣 ቴሌግራም ላይ በቀለስነው https://t.me/selesera አዳራሻችን ታደሙ ☺️

ስለ ስራ!

15 Feb, 12:25


ስራ ፈጠራ እና ስራ ፈጣሪ እየተባለ በተደጋጋሚ ይነሳል።

አንድ ሰው ስራ ፈጣሪ ለመሆን አዕምሮውን፣ አስተሳሰቡን፣ እይታውን እንዴት ማዘጋጀት ይኖርበታል?

ለስራ ፈጠራ አስተሳሰብን መግራት የመጀመርያው እርከን ነው። የዛሬው ርዕሳችን ይህን ይመለከታል።

ለርዕሱ ተገቢውን ምሁር ጋብዘናል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። እንግዳችን ዶክተር ቢላል ሽኩር የቢልኮር ስልጠና ማዕከል መስራች ናቸው።

ዛሬ ቅዳሜ ምሽት 2:45 ጀምሮ በስለ ስራ! ቴሌግራም ቻናል ላይ ይጠብቁን!
https://t.me/selesera

ስለ ስራ! ስራ በእውቀት እንዲሰራ እንተጋለን!

ስለ ስራ!

14 Feb, 14:10


📣 እንዳያመልጣችሁ 📣

እንግዳችን: ዶ/ር ቢላል ሽኩር
ርዕሳችን : የስራ ፈጣሪነት አስተሳሰብ
አድራሻችን: ቴሌግራም ነው

በነፃ 👏

ነገ ቅዳሜ የካቲት 8 ምሽት 2:45 ጀምሮ

ስለ ስራ!

14 Feb, 09:19


የነገ ምሽታችን ከዶ/ር ቢላል ሽኩር በስራ ፈጠራ አስተሳሰብ ላይ ነው ☺️

ዶ/ር ቢላል የ @Bilcor Institute of leadership coaching and Research ሴንተር መስራች፣ አሰልጣኝና የብዙ ሰዎችን አስተሳሰብ የቀየረ፣ ለብዙዎችም አርዓያ የሆነ ምሁር ነው!

☘️ ስራ ፈጠራ ምንድ ነው?
☘️ አጋጣሚዎችን እንዴት ብንቀበላቸው ወደ ቢዝነስ መቀየር እንችላለን?
☘️ ስራ ፈጣሪ መሆን ምን ጥቅም አለው?
☘️ ስራ ፈጣሪዎች ምን አይነት ማይንድ ሴት መላበስ አለባቸው?

የመሳሰሉትን ጥያቄዎች ሊመልስልን ነገ ቅዳሜ የካቲት 8 ምሽት 2:45 ጀምሮ ቀጠሮ ይዘናል።

የአዳራሻችን አድራሻ ስለ ስራ! ቴሌግራም ቻናል ላይ ይሆናል ☺️

መልካም የስራ ቀን!

ስለ ስራ!

14 Feb, 03:33


ነገ ቅዳሜ የካቲት 07 ምሽት . . .

ስለ ስራ!

10 Feb, 08:09


የትርፍና ኪሳራ ''መገናኛ''
===============
አነስተኛ ቢዝነስ ጀማሪዎች ማወቅ ያለባቸው በርካታ ስሌቶች አሉ። አንዱን በምሣሌ እናያለን። ዛሬ ምሣሌ የምንወስደው ደስቲ ባርች ቆንጆ ን ነው። ደስቲ ሲበዛ ፖዘቲቭ አመለካከት ያላት እና የአረብ አገር ሥራዋን ስታጠናቅቅ አነስተኛ ቢዝነሷን አጠናክራ መቀጠል የምትፈልግ የዚህ ሰፈር ድምቀት የሆነች ምርጥ ወዳጃችን ናት። የሬት የፊት ሳሙና የሙከራ ምርት ማምረት ጀምራለች።

ደስቲ የኪሳራ ዞን እና የትርፍ ዞን የት እንደሚገናኙ ማወቅ አለባት። በሌላ አገላለጽ የት መሰነባበት እንዳለባቸው አጥርታ መረዳት አለባት። ይህ መገናኛ/መሰነባበቻ ልዩ ቦታ ''break-even point (BEP)'' ይባላል። ገቢና ወጪ እኩል የሚሆኑበት ወይም ትርፍም ኪሳራም የሌለበት ሊ'ቆይበት የማይገባ 'no peace no war' ዓይነት ሥፍራ ነው። አንድ የቢዝነስ ሰው የት መቆየት እንዳለበት ብቻ ሳይሆን ተረጋግቶ መቀመጥ የሌለበትን ቦታም መለየት አለበት።

ወደ ስሌቱ ስንገባ ደስቲ አጥንታ ተመሳሳይ ሳሙናዎች የሚሸጡበትን ዋጋ ለምርቷ ተመነች - Say ለአንድ ሳሙና 60 ብር (A) ።

ሳሙናዎቹን ለማምረት ፍጆታዎች (Costs) እና ወጪዎች (expenses) አሉባት። እነዚህም ቋሚ (fixed) ወይም ተለዋዋጭ (variable) ሊሆኑ ይችላሉ። ምሣሌ

ቋሚ ወጪዎች (ወርሃዊ)
- የወር ኪራይ 7,000
- ደመወዝና ተያያዥ 12,000
- የመሥሪያ ማሽን
እርጅና ቅናሽ 1,000
ጠቅላላ (B) 20,000

ተለዋዋጭ ወጪዎች በአንድ ሳሙና
- ሬት 10 ብር
- ኮስቲክ ሶዳ 15 ብር
- ቅባት 8 ብር
- ስልክ፣ ውሃና መብራት 2 ብር
- ለመዓዛው (such as
lavender ) 5 ብር
- ፓኬጂንግና ሌብሊንግ 6 ብር
- ማጓጓዣ 4 ብር
የአንድ ሳሙና ተለ. ወጪ (C) 40 ብር

(ዋጋውም ሆነ የወጪዎቹ ዝርዝር ለማሳያ ብቻ የሚውሉ ግምታዊ ቁጥሮች ናቸው።)

የደስቲ break even የሽያጭ መጠኗ በቁጥር
= B ÷ (A - C)
= 20,000 ብር/(80 - 60)
= 1,000 ሳሙናዎች በወር

እናም ከ1,000 በታች አምርታ ከሸጠች 👉 ኪሳራ
1,000 አምርታ ከሸጠች 👉 0 ብር ትርፍ

ስለዚህ አትራፊ ለመሆን በወር ከ1,000 ሳሙናዎች በላይ እያመረተች መሸጥ አለባት። የመሸጫ ዋጋ፣ ፍጆታ እና ወጪዎች ሲጨምሩ/ሲቀንሱ ስሌቱ ሌላ ቁጥር እንደሚያመጣ ልብ ይሏል።

ይቺን ቀላል ስሌት አምራቾች (manufacturers) ብቻ ሳትሆኑ ገዝታችሁ የምትሸጡም (merchandisers) ወይም አገልግሎት ሰጪዎች (Service providers) መጠቀም ትችላላችሁ። ይሁንና ይህ አናሊስስ (Break-even Analysis) አንድ 'መሣሪያ' እንጂ ብቸኛ የትርፍና ኪሳራ አመልካች ስሌት እንዳልሆነ ለመጠቆም እወዳለሁ።
===========
ምሥሉ ላይ የሚታየውን የቁልፍ መያዣ በተለያየ ቅርጽ እንዲሁም ሌሎች ጌጣጌጦችንም መሥራት እንደጀመረች ነግራኛለች። በርቺ ደስቲ እህታችን! 🥰

Dr Hawlet Ahmed

ስለ ስራ!

10 Feb, 07:46


የስለ ስራ! ማህበራዊ ድረ-ገፅ አማራጮችን በመቀላቀልና ለሌሎች በማጋራት ተደራሽነቱን ያስፉ!

👉 FB - Group  https://www.facebook.com/groups/1153093882014917/?ref=share&mibextid=NSMWBT

👉 FB - Page
https://www.facebook.com/profile.php?id=61552032783167&mibextid=ZbWKwL

👉 Youtube - https://www.youtube.com/@SilSira-zs5rw

👉 Tiktok - tiktok.com/@sile.sira

👉 WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029Va5Ch0O9WtBw5eGcdZ3H

👉 Telegram
https://t.me/selesera

ስለ ትብብራችሁ እናመሰግናለን!

ስለ ስራ!

10 Feb, 01:50


በወር ውስጥ ከፍተኛ ተመልካች ካገኙ ፖስቶች መኸከል
ብራቮ ዶክተር አሊኑር አደም

ስለ ስራ!

09 Feb, 16:45


የወሩ ከፍተኛ ተሳታፊዎችና ሌሎች ተጨማሪ ስለ ግሩፑ መረጃዎችን ከምስሉ ይመልከቱ!

ስለ ስራ!

09 Feb, 09:17


የወሩ ከፍተኛ ተደራሽ የሆነ ፖስት

ዶክተር ሙሀመድ ሳኒ 👏

ስለ ስራ!

04 Feb, 03:59


እኛም እናመሰግናለን!
በርቱልን!

ስለ ስራ!

01 Feb, 15:25


እንደምን አመሻችሁ 💫

ውድ የግሩፓችን ተከታታዮች ለዛሬ ምሽት ፕሮግራም አይኖረንም።

ስለ ስራ!

01 Feb, 02:41


ከላይ የሰፈረው ሀሳብ በተመለከተ ኢንጂነር ከፈለኝ ሀይሉ የሰጡት ሀሳብ👇

ስለ ሥራ ማውራት በራሱ ዜጎች ሠርተው ኮርተው እንዲሰሩ ለማስቻል ትልቅ አቅምም እርዳታም ነው ለሚገባው ። አንድ የህይወት ታሪኩን ያጠናሁት ትልቅ ሰው አለ።

ማንም ሰርቶ መብላት ይችላል ።።እጅ የሌለው እግር አለው ይሸምናል ።።አይን አለው ኳሊቲ ኮንትሮል ይሰራል። አይን የሌለው እጅ አለው ። ስጋጃ ይሰራል ።ብዙ ብዙ ነገር ይሰራል ። እኛ ግን እግር የሌለውንም የእኛንም።ሮጠን አሟጠን ወስደን እኛ መፅዋች እሱን ተመፅዋች እናደርግና እንመፃደቃለን ይል ነበር ። ይኽ ሰው ስዊድን አገር በዚሁ ፍልስፍናው ካምፓስ በስሙ ተሰይሞለታል ። ለዓይን ስውራን የሰበታ መርሃ እውራን ት /ቤት ከፍቷል ። ለ ሥጋ ደዌ ህሙማን የ መካኒሳ ዣንጥላ ፋብሪካን ፣ምንጊዜም።ባትሪ ድንጋይን ፋብሪካን ከፍቷል ። የጳውሎስ ሆስፒታልን በዓመት ሁለት ብር በሚከፈል የጤና ኢንሹራንስ ለድኾች ከፍቷል ።።አክሱም በለጥሻቸው ክሊኒክንም ከፍቶ ነበር ። መገናኛ እደጥበብን ለአካል ጉዳተኞች ከፍቷል ። ደርግ አንቆ ገደለው ።

የሱ ፖሊሲና ፍልስፍና በድፍን አውሮፓ use of Residual capacity የሚልን ሃሳብ ወልዶ እንደገና ይህንን ሃሳብ ከአውሮፖ አምጥተን እንጠቀምበታለን ።

ስለ ስራ!

31 Jan, 14:49


#ነፃ #እድል #አሸናፊዎች

የመጀመሪያ ዙር ከስለ ስራ ፌስቡክ ግሩፕ አባላት የነፃ ጥርስ ትጥበት (scaling and calculus cleaning) አምስቱ አሸናፊዎች

ታውቀዋል!!

ለተሳታፊዎች በሙሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን

አሸናፊዎች ባሉት ቀጣይ 7 ቀናት መጥቶ ለመሰራት ቀጠሮ ለማስያዝ @DrTemam ብለው ቴሌግራም ላይ ያግኙን

Winners Also Thanks Too.
አሸናፊዎቹ እንኳን ደስ ያላችሁ

★★
Abdu Sultan ተጨማሪ ሌላ የምትፈልገው ሰው በነፃ ጥርሱ እንዲታጠብ መጋበዝ ትችላለህ (በትላንቱ በፌስቡክ ፔጃችን በነበረውም ሌላ የነፃ ዕድል ላይ አሸናፊ ስለሆንክ)★★

(መስፈርቱ ግን ያው የግሩፕ አባል መሆኑ ነው ወይም ግሩፑን ጆይን እንዲል አስደርገህ እና የኛን ክሊኒክ ፔጅ ፎሎወር ሆኖ)

ዶ/ር ተማም ልዩ የጥርስ ሕክምና ክሊኒክ

ፍላጎታችን ፈገግታዎ ነው

Our Concern Is Your Smile

አዲስ አበባ መርካቶ ሲኒማ ራስ ፊትለፊት ኡራጎ የገበያ ማዕከል 5ኛ ፎቅ ላይ

ስለአገልግሎታችን ለማወቅ

ለበለጠ መረጃ 0973 09 09 09 መደወል ይችላሉ

NB.

በዚህ ዙር ዕድለኞች የተሰጣቸው የጥርስ ትጥበት አገልግሎት መሆኑ ይሰመርበት!!

በቀጣይ ሌላ አገልግሎት ነፃ እናደርግና እናወዳድራለን!!

ስለ ስራ!

31 Jan, 06:48


ስለስራ የተቋቋመው ስለስራና ተያያዥ ጉዳዮች ለመወያየት ነው ☺️

ኖሮን ሰዎችን ብንረዳ አለንላችሁ ብንላቸው ደስ ይለናል 🥺 ነገር ግን ሁሉም ቦታ እንደአላማው ነውና የማሳዘን፣ ተፅዕኖዋቸው የጎላ፣ እንዲሁም በቀጥታ ልመና የሆኑ ፖስቶችን አናሳንፍም። በጭቃኔ አትውሰዱብን አላማችን ስራን ማበረታታት ነውና ልመና ከአላማችን ጋር ይጋጫል!!

ከዚህ በተጨማሪ ፖስቶች ሊንክ ካላቸው፣ የውጭ ሀገር የስራ እድል የሚሉ፣ ባጠቃላይ ማጭበርበር ናቸው ብሎ ካመነ የፌስቡክ አሲስታንስ ሲስተም አውቶማቲካሊ ያጠፋዋል!! ☺️ (በርግጥ አንዳንዴ በስህተት ትክክለኛዎቹንም ያስወግዳል፣ ከአቅማችን ውጪ ስለሆነ እንጂ)

በተያያዘ ፖስቶችን ስትልኩ ግልፅና ሙሉ መረጃ ያለው ቢሆን ይመረጣል። ድፍንፍን ያለ ከሆነ ከአላማችን ጋር ይጋጫል አይጋጭም የሚለውን ማወቅ ስለሚቸግረን ወይ እናስወግደዋለን!

👍ግዙ፣ ሽጡ፣ ሀሳብ ተለዋወጡ - በመከባበር
👍 ተረዳዱ ተደናነቁ፣ ሞራል ተገነባቡ - በመተጋገዝ መንፈስ

ቤታችን ቤታችሁ ነው የተሰማችሁን ንገሩን!
#ስራ_በእውቀት_እንዲሰራ_እንተጋለን

ስለ ስራ!

29 Jan, 12:17


#ነፃ የጥርስ ትጥበት ህክምና #ቻሌንጅ
#ከዶክተር ተማም የጥርስ ሕክምና ክሊኒክ

የመጀመሪያ ዙር #group_challenge

ይህ ማስታወቂያ ከተፖሰተ ለሁለት ቀናት(48 ሰአት) ብቻ የሚቆይ ነፃ የትጥበት Give Away። ውድድሩ ከ125ሺ በላይ አባላት ላሉት "ስለ ስራ!" የፌስቡክ ግሩፕ ላይ ይካሄዳል።

ለአምስት (5) የግሩፕ አባላት ብቻ የተሰጠ ነፃ ጥርስ እጥበት (scaling and calculus cleaning)!!!

የውድድሩ መስፈርት

1. የስለ ስራ! ግሩፕ ቴሌግራም ቻናልን ጆይን ማድረግ https://t.me/selesera

2. ዶ/ር ተማም የጥርስ ሕክምና ክሊኒክ ፌስቡክ ፔጅ ፎሎው ማድረግ
https://www.facebook.com/share/14fX1UGizV/

3. ኮሜንት ላይ ጠቃሚ የምትሉትን ሀሳብ በማስፈር መወዳደር ይቻላል

4. ከፍተኛ የላይክ ቁጥር ያገኘ አሸናፊ ይሆናል

አሸናፊዎች ከታወቁ ቡኋላ በቀጣይ ባሉት 7 የስራ ቀናት ውስጥ የነፃ ጥርስ ትጥበቱ እንዲሰራላችሁ inbox ላይ ቀጠሮ ያሲዛሉ!

ፍላጎታችን ፈገግታዎ ነው - Our Concer Is Your Smile

ዶ/ር ተማም የጥርስ ሕክምና ክሊኒክ
አድራሻ፦ አዲስ አበባ፣ ሲኒማ ራስ - ኡራጎ የገበያ ማዕከል 5ኛ ፎቅ

ስለ ስራ!

27 Jan, 04:14


ተዘግቷል🙏 ሁላችሁንም እናመሰግናለን።
አንድ ጊዜ ለራሳችሁ ሞራል👍🤝👏

ስለ ስራ! የተመሰረተበትን ሁለተኛ አመት ምክንያት በማድረግ ሶስተኛ ዙር ለአምስት ተከታታይ ቀናት በስለ ስራ! ፌስቡክ ግሩፕ ስናደርገው የነበረው የትውውቅ ፕሮግራም ተጠናቋል።

ትውውቁ ግሩፓችን የያዘውን እምቅ አቅም የተረዳንበት ሆኖ አልፏል። ከሁሉም አከባቢና ማህበረሰብ፣ ከተለያየ የስራ መስክ፣ የፆታና እድሜ ተዋፅኦ፣ የተለያየ ልምድና የትምህርት ደረጃ መኖሩን ተገንዝበናል።

ግሩፑ በአግባቡ ከተመራ ትልቅ ደረጃ መድረስ እንደሚችል ከቀና አስተያየቶቻችሁ ለመረዳት ችለናል።

ራሳችሁን ያስተዋወቃችሁ፣ በላይክ፣ ኮሜንትና በመሳሰሉት እገዛና ሞራል የሰጣችሁ በሙሉ እናመሰግናለን።

ግሩፑ የናንተው ነው። ህግና ደንቦች ይከበሩ። አባላቶች እንወዳቹሀለን፣ እናከብራቹሀለን።

መልካም የስራ ጊዜ🖐

ስለ ስራ!

27 Jan, 04:04


ውድ ስለ ስራ ቤተሰቦች

አህመድ ኡመር እባላለሁ

የፊዚክስ መምህር ስሆን የመጀመርያ ድግሪየን በ Applied Physic 2001 እና ሁለተኛ ድግሪ MS.C in atomic and molecular  physics 2003 በድላ ዩኒቨርስቲ ተመርቄያለሁ።

ከ2004 ጀምሬ በድሬደዋ የኒቨርስቲ እያገለገልኩ እገኛለሁ።

የ Ph.D ትምህርቴን በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርስቲ በማጠናቀቅ ላይ  የምገኝ ስሆን ሪሰርቸን በሶላር ኢነረጅ ላይ እየሰራሁ እገኛለሁ። በዚሁ ፊልድ ከ16 ወረቀቶችን አሳትሜለሁ። በሪሰርች የማማከር ስራ እሰራለሁ። ኮምፒውቴሺናል ፊዚክስ እችላላሁ።  ስልጠናም እሰጣለሁ።

በቢዝነስ ዘርፍም አለሁ ምርጥ እንጀራና ባልትና አቀርባለሁ። እንጀራ ለዝግጅትና ለሆቴል አቀርባለሁ። ሽሮ፣ በርበሬ፣ በሶ፣ የአጥሚትና የገንፎ እህልም እናቀርባለን።

እዘዙን ታዛዥ ነን።

አድራሻ  ድሬዳዋ፦ 0962626590 ይደውሉ ያላችሁበት እናደርሳለን።

ስለ ስራ!

27 Jan, 04:00


ኢክራም አብዱልዓዚዝ እባላለሁ። ተወልጄ ያደግኩት አዲስ አበባ መካኒሳ አካባቢ ነው።አሁን ላይ የ4ኛ ዓመት ተማሪ ነኝ። ለመመረቅ ድፍን 2 ዓመታት ይቀሩኛል።

ግን ሌላ ሚስጥር አለ! በካሊግራፊ እና በአርት ዓለም ውስጥ እየተንሸራሸርኩ ነው። ከልጅነቴ ጀምሮ ስኬች ማድረግ፣ ማስመር፣ ማሳመር፣ መሳልና መጻፍ እወድ ነበር። እናም ከትምህርቴ ጎን የቀለም ህጎችንና መሰል የአርት ዘርፎችን በመማር ተመርቄ ልምዶችን አዳብሪያለሁ አልሐምዱሊላህ።

ሌላው አካዳሚካሊም ፋይናንሺያሊም ግራጁዌት ማድረግ ስለምፈልግ/ስላለብኝም ከትምህርቴ ጎን ለጎን እነዚህን እና መሰል ውብ የካሊግራፊና አርት ስራዎችን በኦርደር እሰራለሁ።

የእጅ ስራዬን ለእናንተ፣ ለቤታችሁ፣ ለቢሯችሁ፣ ለክፍላችሁ፣ ለመስጂድ፣ ለምርቃት፣ ለወዳጅነት አበርክቶ፣ ለሽልማት፣ ለጫረታ እንዲሁም ለተለያዩ ፕሮግራሞች፣ ለተጋቢዎች ትርጉም ያለው ስጦታ ኢክራም ማድረግ ስትፈልጉ @ikramabdulaziz ብላችሁ ቴሌግራም ላይ ብታወሩኝ አሊያም በ0960281050 ብትደውሉ ታገኙኛላችሁ።

በካንቫስ፣ በMDF፣ በቆዳ፣ በመስታወት፣ በጨርቅና በፍሬም በመረጣችሁት ማቴሪያል በደስታ እሰራላችኋለሁ! ተሐዱ ተሐቡ! ተሰጣጡ ትዋደዳላችሁ😊♥️

ስለ ስራ!

27 Jan, 03:59


ሰላም የ ስለ ስራ ቤተሰቦች!

ገሜ እባላለው የ Maroset ፕላትፎርም Technical Assistant ነኝ። Maroset ብቸኛው የርቀት ስራዎች ብቻ የሚለቀቁበት ኢትዮጵያዊ ፕላትፎርም ነው፥ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮም ብዙ ባለሞያዎችን ከ ቀጣሪ ድርጅቶች እና ግለሰቦች ጋር አገናኝቷል። ፕላትፎርሙ በዋናነት ቴሌግራም ቻናል Maroset በሚለው username እየሰራ ሲሆን እንዲሁም በድህረ ገፅ /Website maroset.com ላይም የርቀት ስራዎች ይለቀቃሉ።

እንኳን ወደ Maroset ፕላትፎርም በሰላም መጡ። ይህ ፕላትፎርም ባለሞያዎች ጊዜ እና ቦታ ሳይገድባቸው ባሉበት ሆነው በኦንላይን ዘርፈ ብዙ የስራ ዕድሎች ላይ ተቀጥረው መስራት የሚችሉበት እንዲሁም ቀጣሪዎች ወይም አሰሪዎች በኦንላይን ብቁ ባለሞያዎችን ቀጥረው ማሰራት የሚችሉበት ምቹ መድረክ ነው።

በዚህ ፕላትፎርም ሁሉም ስራዎች የሚሰሩት በኦንላይን ባሉበት ሆነው ነው።

https://t.me/Maroset

ስለ ስራ!

26 Jan, 20:33


የሁለት አመት ጉዞ - ስለ ስራ!

ፌስቡክ ግሩፕ --------- 123ሺ በላይ
(አንድ መቶ ሀያ ሲስት ሺ አባላት)

ፌስቡክ ፔጅ  ---------- 1650 +

ቴሌግራም ገፅ ---------- 6950+ አባላት
(https://t.me/selesera

የስለ ስራ! ግሩፕ አድሚኖችን ያውቋቸዋል?
ተወዳጇቸው!

Zubeyda Awel ( @Zubenet
Ezedin Sultan  ( @ezedin92
ሉላ ኢሳ ( @Yeamalenat
Mubarek Sadik ( @Ibnusadik
Ina Omer ( @Inuyaa
Bin Ali ( @wdiali
ስለ ስራ ( @Selesera_bot

ሁለት አመታት ከናንተ ጋር በመዝለቃችን ደስታ ይሰማናል።

ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

26 Jan, 20:32


ሰላም ሰላም
ዳሃብ ያሲን እባላለሁ ጋዜጠኛ ነኝ ::እድገቴ አክሱም እና አዳማ ነው ::ትምህርቴንም ሁለቱም አካባቢዎች ላይ ተምሪያለው ከ 10ኛ ክፍል አቋርጬ ሳዑድ አረብያ የሄድኩ ቢሆንም ከ 4 ዓመት በኅዋላ ተመልሼ ትምህርቴን አጠናቅቂያለው ::(ይቻላል ለማለት ነው )
ከ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በ ጋዜጠኝነት የ መጀመሪያ ዲግሪ አለኝ ::
በ አሁን ሰዓት በ ሬድዮ እና በ Etv እየሰራሁ እገኛለው ::
በ ትርፍ ሰዓቴ ማህበረሰብ ተኮር የ ሬድዮ ድራማዎች የ ድምፅ ማስታወቂያዎች በተለያየ ቋንቋ (ዓረብኛ :ትግርኛ :አማርኛ )እሰራለሁ ::

በ መጨርሻ ሰዓት ስለ መጣሁ 10 ለሚሆኑ ድርጅቶች የ ድምፅ ማስታወቂያ በ ነፃ ለመስራት ዝግጁ ነኝ ::

ስላወቅኳችሁ ደስ ብሎኛል አመሰግናለው 🙏

ስለ ስራ!

26 Jan, 20:20


ሰላም የስለ ስራ ግሩፕ አባላት እነደምን አላችሁ
ውብሊቀር እሱቤ እባላለሁኝ በ 2012 ዓ.ም ከአ.አ.ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ በመካኒካል ምህንድስናን የተመረቁት
አሁን በ CNC ማሽን ኦኘሬተር እና ዲዛይነርነት እየሰራሁ እገኛለሁ።
እና 3D,2D design and drawing በ Solidwork, CamBam software እሰራለሁ።

በ cnc machine ብረት(ላሜራ)ከ0.5-20mm thickness ማስቆረጥ የሚፈልግ ወይም ዲዛይን ማሰራት የሚፈልግ እና ለበለጠ መረጃ
0946353328 ሃሎ ይበሉ!

ስለ ስራ!

26 Jan, 19:56


ግሩም ተ/ሀይማኖት እባላለሁ። ለትውውቅ ብዘገይም ለወዳጅነትና ስራ ፈጣን ነኝና በይቅርታ ልጀምር።
ጋዜጠኛና ደራሲ ነኝ። ከሀያ ሰባት በላይ ልምድ አለኝ። በዛ ያለውን እድሜዬን በህትመት ሚዲያ ላይ ነው ያሳለፍኩት። አራት መጽሐፎችን አሳትሜያለሁ። ያላሳተምኩት ሰባት መጽሐፍ አለኝ። በተለይ ያልተነገሩ የኢትዮጵያ ታሪኮች የሚል መጽሐፌ ህትመት ሊገባ ከተዘጋጀ በኋላ የወረቀት ዋጋ በመጨመሩ አሳታሚዎች ገበያ ፈርተው እንዲሁ ቀትቷል። ከአንጋፋ ደራሲዎች ጀምሮ እስከጀማሪዎች በርካታ መጽሐፎች አርትኦት ሰርቻለሁ። አርትኦት አሁንም እሰራለሁ። የሚፈልግ ካለ ያግኘኝ።

በጽሑፉ ሁለት በኩል ተከታታይ ድራማዎችን፣ ሶስት የሙሉ ሰዓት ፊልሞችንና ጭውውቶችን ብጽፍም ወደ ፊልምነት ለመቀየር አልጣርኩም። ትወና፣ ዝግጅት፣ ቴያትር ሰርቼ አውቃለሁ ግን አልገፋሁበትም። አሁን ግን ሀሳብ አለኝ።
በርካታ ሬዲዮ ጣቢያዎች ዶቼዌሌ (ጀርመን ሬዲዮ) ቪኤኤ ሳይቀር ከየመን በሪፖርተርነት ሰርቻለሁ። ሀገሬ ከገባሁ ጀምሮ ግን የሬዲዮ ነገር ወፍ የለም። ግን መስራት እፈልጋለሁ። ማንኛውንም ነገር የሚፈልግ በውስጥ ያውራኝ።

ስለ ስራ!

26 Jan, 19:55


ሰላም ጀመአ እንዴት ናቹ ስሜ ዚያድ ልጀባ እባላለሁ እድሜዬ 21 ሲሆን ትምርት ብዙም ያልተማርኩ በ 10ክፍል በ 2011 አqarche በቡቲክ ሥራ ተቀጥሬ በመለስተኛ ደሞዝ ከዘመድጋ እስራለሁ ሳሪስ አካባቢ ያላችሁ የዚ ግሩፕ አባል ወንዶች ታላቅ ቅናሽ አለላችሁ ኑና ዘይሩን...😍

ስለተዋወካቹ በጣም ደስ ብሎኛል 🥰

ስለ ስራ!

26 Jan, 19:40


ዶክተር አሊኑር አደም
0911554534

ስለ ስራ!

26 Jan, 19:19


ም/ሳጅን አብዱራህማን አብዱልመናን እባላለሁ። ተወልጄ ያደኩት ሰ/ወሎ ሀራ ከተማ አስተዳደር ነው። በሙያየ የፌደራል ፖሊስ አባል እና አጃቢም ነኝ። ፌስቡክን ለ14 አመት በላይ የተጠቀምኩበት ሲሆን ብዙ ጥሩ ወዳጆችንና እህት ወንድሞችን እንዲሁም ውዷን ባለቤቴን ተዋውቄ አግብቼበታለሁ 😃
በስራየ ላይ ሰዎች እንዲበደሉ አልፈልግም፣ሰዎችንም አልበድልም፣ ፍትህን አሰፍናለሁ። ማናችሁም ፖሊሳዊ ችግርና ጥያቄ ሲኖራችሁ ብታናግሩኝ በቻልኩት አቅም ጥሩ መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ አመሰግናለሁ።

ስለ ስራ!

26 Jan, 19:18


በመጀመሪያ ለውድ ለአድሚኖች እና አባላት ሰምታዬን አቀርባለሁ ስለ ተዋወቅን ደስ ብሎኛል ። ስሜ አብዱለጢፍ ዩሱፍ እባላለሁ ትውልዴ ጉራጌ ዞን ሲሆን ያደኩት እና በአብዛኛው የተማርኩት አዲስ አበባ ነው።

የትምህርት ደረጃዬ ከአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በ chemical engineering የመጀመሪያ ዲግሪ ሲኖረኝ ከ ጀነራል ዊንጌት በ road construction and maintainance level 4 certificate አለኝ ።

በሙያዬ በመንገድ ንጣፍ እና እድሳት የሰራሁ ሲሆን በ ኬሚካል ምህንድስናም የተለያዩ የግል እና የመንግስት ድርጅቶች ላይ ሰርቻለሁ። በዚህም እንደ ኢትዮጰያ አከባቢ ጥበቃ ባለስልጣን እነዲሁም SilAfrica industrial limiteds በሚባል የውጭ ግል ድርጅት ውስጥ የሰራሁ ሲሆን አሁን ላይ Maticline industrial limiteds በሚባል ድርጅት ውስጥ በproject ማናጀርነት እየሰራሁ እገኛለሁ።

ድርጅታችን #Maticline በቻይና ሀገር መቀመጫውን በማድረግ የተለያዩ ማሽነሪዎች የሚያመርት ሲሆን አሁን ላይ ለየት ያለ ደንበኛ ተኮር አገልግሎት እየሰጠን እንገኛለን ። በተለይም በ manufacturing ዘርፍ ለመሰማራት የፈለጋችሁ ሁሉ አቀፍ አገልግሎት በመስጠት በ project ግምገማ እና design , project planing ጨምሮ ድህረ ምርት ሽያጭ እና ገበያ ላይ ከበቂ ማማከር አገልግሎት ጋር ዘመኑ ያፈራውን እና ሀይል ቆጣቢ ማሽነሪዎችን እናቀርባለን ።በአጠቃላይ በ manufacturing ዘርፍ የተለያዩ ማሽኖችን ማምረት እነ installation , commissioning እና የነፃ maintainance እንሰጣለን ። ከነዚህም በተለይም
የ bottled water (እሽግ እና ጃር ) water ማምረቻ
የወተት እና ወተት ተዋፅኦ ማምረቻ
የማንጎ ጁስ እና ለስላሳ መጠጦች ማምረቻ
የቲማቲም ድልህ (tomato paste ) ማምረቻ
ሳሙና , የገበያ ላርጎ እንዲሁም cosmetic product ማምረት,
በ ጄሪካን እና plastic bottle injection ማሽኖችን ማምረትን ጨምሮ ማንኛቸውም ፈሳሽ ምርቶችን እና ማሸጊያዎች ለማምረት ስትፈልጉ እና ከበቂ ድጋፍ ጋር እንደ ቤተሰብ እናወያያለን ፤ እናቀርባለን ።

በተጨማሪም ከዘርፉ ጋር ተዛማጅ የሆኑ ስራዎች እንደ steel መጋዘን , እንደ ጥሬ እቃ እና packaging lable, film የመሳሰሉትን ከአምራቾች ጋር እናገናኛለን።

ስልክ 0913371159/0967973067
e mail : [email protected]

ስለ ስራ!

25 Jan, 04:52


ጥያቄ እና ምላሽ

ጥ፦ ስለ ስራ! ላይ እየተደረገ ያለው ትውውቅ መች ይጠናቀቃል?
መ፦ ትውውቁ ዛሬ ቅዳሜ ጥር 17/2017 ምሽት 2:45 ላይ ይጠናቀቃል።

ጥ፦ ትውውቁ ላይ ማን ነው ተሳታፊ መሆን የሚችለው?
መ፦ ሁሉም የግሩፑ አባል ያለ ልዩነት ተሳታፊ መሆን ይችላል

ጥ፦ ተደጋጋሚ ጊዜ ለጥፈን ውድቅ ተደርጎብናል። የተለየ መስፈርት ይኖር ይሆን?
መ፦ ለትውውቁ የተለየ መስፈርት የለም። ነባር 10ሩ የግሩፑ ህጎች ናቸው ተግባራዊ የሆኑት።

ጥ፦ በተደጋጋሚ ውድቅ የሚሆንበት ምክንያት ምን ይሆን?
መ፦ የሚላኩ ፖስቶች ሊንክ(link) ካላቸው Admin Assist ውድቅ ያደርጋቸዋል። ሊንክ ፖስት ላይ ሳይሆን ኮሜንት ላይ መጠቀም ይቻላል።

ጥ፦ ስለ ግሩፑ መረጃ ወይም ጥያቄ ቢኖረን ማንን እንጠይቅ?
መ፦ ከ6ቱ የግሩፑ አድሚኖች ማሳወቅ ወይም መጠየቅ ትችላላችሁ።

ጥ፦ ከስለ ስራ! ቀጣይ ምን እንጠብቅ?
መ፦ ስለ ስራ! የተመሰረተበትን ሁለተኛ አመት በማስመልከት በቅርቡ በአዲስ ነገር ይከሰታል። ጊዜው ሲደርስ እናሳውቃለን። እስከዛው በንቃት ጠብቁን።

ጥ፦ ስለ ስራ! ፌስቡክ ላይ ሌላ የተከፈተ ግሩፕ አለው?
መ፦ የለውም። ትክክለኛውና ቀዳሚው የስለ ስራ! ግሩፕ ከ122ሺ በላይ አባላት ያሉት private ግሩፕ ነው። ስለ ስራ! ከሚለው ስያሜ ቀጥሎ "!" (ቃል አጋኖ) ምልክት ስላለው በቀላሉ መለየት ይቻላል።

ጥ፦ ስለ ስራ!ን ከፌስቡክ ውጭ በየትኛው ማህበራዊ ድረ-ገፅ ማግኘት ይቻላል?
መ፦ በሁሉም ማህበራዊ ድረ-ገፆች ይገኛል። ይበልጥ በተለያዩ የቢዝነስ ርዕሰ ጉዳዮች ባለሙያዎች እያጋበዘ የሚያቀርብበትን የቴሌግራም ቻናል ቢቀላቀሉ ብዙ ያተርፋሉ።
https://t.me/selesera

እናመሰግናለን! @ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

24 Jan, 18:52


መልካም ግብዣ ለሁላችሁም!

ርዕስ ፦ የወተት ልማት በኢትዮጵያ

ሁላችሁንም ጋብዘናል

ቅዳሜ ጥር 17/2017 ከምሽቱ  2:45 ላይ በቀጥታ ስርጭት በስለ ስራ! ቴሌግራም ቻናል ላይ እንገናኝ ።

አቅራቢ 👉 ዶክተር ጀይሉ ጀማል በሽር
(በኢትዮጵያ የግብርና እና ምርምር ኢንስትቲዮት ባዮቴክኖሎጂ ምርምር ማዕከል ከፍተኛ ተመራማሪ)

አወያይ 👉  ኢዘዲን ሱልጣን   

ቦታ 👉  https://t.me/selesera

ሰዓት 👉 በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 2:45

ሀሳብና ጥያቄዎችን የምታቀርቡበት እድሎች ተመቻችተዋል። ሊንኩን ሼር በማድረግ ይቀላቀሉን! 

👉 Telegram
https://t.me/selesera

ስራ በእውቀት እንዲሰራ እንተጋለን!
@ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

24 Jan, 18:51


#Ethiopia

ግምሩክ ኮሚሽን አምራቾች ወደ አገር ዉስጥ እቃዎችን ሲያስገቡ በሚያቀርቡት ህጋዊ የግብይት ዋጋ ብቻ እንዲስተናገዱ ፈቅዷል።

ኮሚሽኑ በአምራቾች ወደ አገር ዉስጥ የሚገቡ ዕቃዎች የዋጋ አተማመን ስርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታውቋል።

158/2011 የተደነገገውን በጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ማስከፈያ ዋጋ አተማመን መመሪያ እንዲከለስ ማድረጉን ነዉ የተገለጸው።

ይህ መመሪያ በአምራቾች ወደ አገር የሚገቡ ዕቃዎች ዋጋ በሚወስንበት ወቅት የሚወስደው ጊዜ ከአምራቾች ከፍተኛ ቅሬታ እያስነሳ ይገኛል።

ይሄን ተከትሎ በአምራቾች ወደ አገር የሚገቡ ዕቃዎች ዋጋ አተማመን ሥርዓት ላይ ማሻሻያ ማድረግ ማስፈለጉን ተነግሯል።

መመሪያ ቁጥር 158/2011 እስኪሻሻል ድረስ በክሊራንስ ጊዜ የዋጋ ማጣራት ሃደቱ የሚወስደውን ጊዜ ለማስቀረት በሚል አምራቾች እቃዎችን ወደ አገር ውስጥ ሲያስገቡ በሚያቀርቡት ህጋዊ የግብይት ዋጋ እንዲስተናገዱ ኮሚሽኑ በላከው ሰርኩላር ፈቅዷል።

ይህ ሰርኩላር ፦
- አምራቾች
- ልዩ መብት የተሰጣቸው የኢኮኖሚ አንቀሳቃሽ ፕሮግራም ተጠቃሚ ድርጅቶች፥
- ለኢንቨስትመንት ሥራ ዕቃዎችን በቀረጥ ነፃ የሚያስገቡ ድርጅቶች፤
- የመንግስት ፕሮጀክትን ለመስራት በግል ድርጅቶች የሚገቡ ዕቃዎች፣
- የመንግስት የልማት ድርጅቶች እና የፌዴራልና የክልል መንግስታት ተቋማትን ይመለከታል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካቲፓል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

24 Jan, 16:38


ሙስጦፋ አብደላ እባላለሁ። የኢኮኖሚክስ ባለሙያ ነኝ። ከ20 ዓመት በላይ የስራ ልምድ አለኝ። በኢኮኖሚ በቢዝነስ እና በኢንቨስትመንት ጉዳዮች አማካሪ ነኝ። በብዙ ዘርፎች ስልጠናዎችን ሰጥቻለሁ። ሃገር አቀፍ ስልጠናዎችም ላይ National Trainer በመሆን ሰርቻለሁ። UN ን ጨምሮ በተለያዩ NGOዎች በProject ሃላፊነት ሰርቻለሁ። የተለያዩ የResearch ስራዎች ላይ የተሳተፍኩ ሲሆን ከColumbia University ፕሮፌሰሮች ጋር በመሆን የሰራሁት አንድ ጥናት በAmerican Journal ወጥቷል። እስካሁን ወደ ስድስት የሚሆኑ መጽሐፎች ጽፌያለሁ። ፎርቹን ጋዜጣን ጨምሮ በተለያዩ መድረኮች በኢኮኖሚክስ እና በቢዝነስ ጉዳዮች ሃሳብ በመስጠት እታወቃለሁ። ከዚህ ዋና ሞያዬ በተጓዳኝ ሌሎች ሞያዎችም አሉኝ። ለተወሰነ ዓመታት በሶፍትዌር ዲቨሎፕርነርነት ሰርቻለሁ። ብዙ ሶፍትዌሮችን የሰራሁ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ሁለቱ ከኢትዮጵያ አእምሮእዊ ንብረት ጽ/ቤት ፓቴንት አግኝቼባቸዋለሁ። ከ60 በላይ ለሚሆኑ ትልልቅ የንግድ ተቋማት ዌብሳይት ዲቨሎፕ አድርጌለሁ። አሁንም እሰራለሁ። አምስት ያህል ዶክሜታሪ ፊልሞችን ለተለያዩ ተቋማትና NGOዎች በዳይሬተርነት አዘጋጅቻለሁ። ከጅማ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር በወጣቶች ላይ የሰራናቸውን ስራዎችን ጨምሮ በተለያዩ ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ተሳትፌያለሁ።
ዋናው ስራዬ ግን በቢዝነስና በኢንቨስትመንት ጉዳዮች ማማከር ነው። በትምህር ዝግጅቴም በኢኮኖሚክስ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን እና በሌሎች ዘርፎች ማስተርስ እና ዲግሪዎች አሉኝ። አዲስ አበባ ዩኒቨስቲ እና ጅማ ዩኒቨርስቲን ጨምሮ በተለያዩ ተቋማት ተምሪያለሁ። Interest Free Bankingን ጨምሮ ከ20 በላይ ሰርቲፊኬሽኖች አሉኝ። በአሁኑ ጊዜ የዛፈር ፕላስ የቢዝነስ እና ኢንቨስትመንት የማማከር አገልግሎት CEO ነኝ። ከጀማሪ ቢዝነሶች እስከ ትላልቅ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች እያማከርን እንገኛለን። ከBusiness Idea ጀምሮ ቢዝነስ ማቋቋምን ጨምሮ ትላልቅ የቢዝነስ ችግሮችን እስከ መፍታት ብዙ ሰርቪሶችን እንሰጣለን። አጫጭር የቢዝነስ ስልጠናዎችንም እንሰጣለን። ጠንካራ የቢዝነስ አማካሪዎች team በማቋቋም እነዚህን እና ሌሎች በርካታ አገልግሎቶችን እየሰጠን እንገኛለን።
የቢዝነስ ማማከር አገልግሎት
የኢንቨስትመንት ማማከር አገልግሎት
አጫጭር የቢዝነስ ስልጠናዎች
የቢዝነስ ሃሳቦች ማመንጨት (Business Ideation)
·የአዋጭነት ጥናት (Feasibility Study) መስራት
. . .
በዚህ ስልክ 09 11 23 23 22 እንገኛለን

ስለ ስራ!

24 Jan, 16:32


ስሜ ዶ/ር መሀመድ ሰዒድ፣ አሁን የምኖረው ድሬዳዋ፣

የትምህርት ዝግጅት፡ በ 2009 በህክምና ዶክትሬት ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በ2015 የቀዶ ህክምና ስፔሻሊቲ ትምህርት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ተከታትያለሁ።

የስራ ልምድ፡ እንደተመረኩ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በክሊኒካል አስተባባሪነት ለ አንድ ዓመት ካገለገልኩ በኋላ በ 2011 ለስፔሻሊቲ ትምህርት ወደ ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በማቅናት 4 ዓመት ከተከታተልኩ በኋላ ወደ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመመለስ የተለያዩ ስራዎችን ሰርቻለሁ።

ከነዚህም ዉስጥ የክረምት በጎ አድራጎትን  ማለትም ነጻ የጤና ምርመራዎችንና የጤና ትምህርቶችን በማስተባበር እንዲሁም አዲስ የጀመረውን የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ስራ እንዲጀምር ለማስቻል የነበረውን ጥረት በመደገፍ የበኩሌን አበርክቻለሁ (አላህ እንዲቀበለኝ ዱዓ አርጉልኝ)።

ሆስፒታሉ ከጀመረበት እለት ጀምሮ ለ 10 ወራት በህክምና ትምህርትና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር (በድሮው ሜዲካል ዳይሬክተር) በመሆን አብረዉኝ ከነበሩት የስራ ባልደረቦቼ ብዙ የአስተዳደር (Leadership) ክህሎቶችን አግኝቻለሁ።

ከመንግስት መስሪያ ቤቶች ዉጭ ደግሞ በ ሆዮ የእናቶችና የህጻናት ክሊኒክ (Hoyo MCH) እንዲሁም በኢፍቱ ሆስፒታል የተለያዩ መለስተኛና ከፍተኛ የቀዶ ህክምናዎችን እሰጣለሁ።

እንዲሁም ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለጳውሎስ ሆስፒታል በተጻፈልኝ የድጋፍ ደብዳቤ የአጭር ጊዜ ስልጠና በመውሰድ የኩላሊት ድክመት ላለባቸው ታካሚዎች የሚያስፈልገዉን የደም ስር የማያያዝ ቀዶ ህክምና (AVF) በኢፍቱ ሆስፒታል ለመስራት ዝግጅታችንን ጨርሰናል።

ከቀዶ ህክምና ጋር የተያያዘ ህክምና ካስፈለገዎት ከስር ባለው ስልክ መደወል ይችላሉ።

📱ቁጥር= 0910340800

ስለ ስራ!

24 Jan, 15:11


አቤሴሎም መለሰ እባላለሁ። በኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ ሲነዬር ሲቪል መሀንዲስ ነኝ። ሙያዬን ስለምወደው በኢትዮጵያ በቴሌቪዥንና fm 97.1 Eva Show et media በኮንስትራክሽን በኢኮኖሚ ጉዳዮች ፕሮግራም እያዘጋጀሁ አቀርባለሁ።

በማንኛውም የግንባታ ማማከር ጉዳዮችና በሚዲያ የማስታወቂያ ስራዎች አብሮኝ መስራት የሚፈልግ ካለ በደስታ እቀበላለሁ!

Facebook page Eva Show et media

My YouTube page
👇👇
https://www.youtube.com/@evashow10

my business tiktok
👇👇
tiktok.com/@evashowcon

Thank u bro🙏

ስለ ስራ!

24 Jan, 14:10


#2 #ቀናት #ብቻ #ቀሩት

አያምልጥዎ

አባላት #የዲስካውንት ዕድሉን እየተጠቀሙበት ነው !!! እርስዎስ?

ለ"ስለ ስራ!" ግሩፕ አባላት የተሰጠው ለአንድ ወር 10% የጥርስ ህክምና ዲስካውንት ማብቂያ ጊዜው ተቃርቧል #ጥር 18 /2017 ነው

0973 09 09 09 ላይ
ፈጥነው ይደውሉ አሁኑኑ ቀጠሮ ያስይዙ!

የፖስቱን ስክሪን ሹት መያዝ በቂ ነው

Dr Temam Speciality Dental Clinic ዶ/ር ተማም ልዩ የጥርስ ሕክምና ክሊኒክ

አዲስ አበባ መርካቶ ሲኒማራስ ፊትለፊት ኡራጎ የገበያ ማዕከል 5ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን

ፍላጎታችን ፈገግታዎ ነው

Our Concern Is Your Smile.

ስለ ስራ!

24 Jan, 13:45


ሰላም ለዚህ ቤት የትውውቅ ቻሌንጅ መኖሩን ሰምቼ ነው 🥰 እንተዋወቅ ኢየሩሳሌም እባላለሁ ንፁህ ኢትዮጵየዊት ነኝ የ21 አመት ወጣት ስሆን የሶስተኛ አመት የ Ho 🥼💉🌡💊እንዲሁም በ ኢክስቴሽን ፕሮግራም የ Marketing management ተማሪ ነኝ መማር ውስጤ ነው 😍 የ Graphics designing እና ለፕሮግራሞች ዲኮር የመስራት ችሎታም አለኝ 🥰 ባለችኝ ጊዜ በ Online የወንድሜን ስራ በማስተዋወቅ ደንበኛ በማምጣት የማርኬቲንግ ተማሪነቴን አስመስክሪያለሁ🥰😍 እናንተም ከኛ የፈርኒቸር ውጤቶችን በመግዛት አበርቱን
☎️09-54-14-39-19 በመደወል እዘዙን በደስታ እናስተናግዳለን ደህና ሁኑልኝ🥰

ስለ ስራ!

24 Jan, 12:26


እንተዋወቅ
ስሜ ንግስት ወ/ገሪማ ይባላል የቆሎ ሀገር በሆነችዉ ደብረሲና ነዉ ተወልጄ ያደኩት በእዚሁ አጋጣሚ ቆሎ ከፈለጋችሁ አለኝ እና በጤናዉ ዘርፍ የላብራቶሪ ባለሙያ ነኝ ደግሞስ አትሉምጎን ለጎን ኑሮን ለማሸነፍ ቆንጆ ቆንጆ ከህፃን -አዋቂ የጋርመንት qualit3የሆኑ ቱታዎችን በ online እሸጣለሁ በእዚሁ አጋጣሚ ህትመት ቤት ማች ለ church ለሀዘን ለተለያዪ ፕሮግራሞች ቲሸርቶች ስትፈልጉ እዘዙች ያላችሁበት ድረስ አመጣለሁ ...ቢሳካልኝ ብዙ ነገሮች መስራት ፈልጋለሁ social midia lay ጎበዝ ነኝ እና ነጋዴዎች አሰሩኝ ማደግ ፈልጋለሁ እናም መርቁኝ እስኪ የራሴ ሱቅ እንዲኖረኝ🙏🙏🙏አመሰግናለሁ🙏🙏🙏

https://t.me/NIGSTWOLDE21

ስለ ስራ!

24 Jan, 12:22


ሥሜ ዳዊት እባላለዉ
የምሠራወዉ ሥራ ኮንስትራክሽን ነዉ
ከምሠራዉ ስራም መካክከል ጎበዝ የብሎኬት ስራተኛ ነኝ በተሠጠኝ ግዜ ገደብ እና በተመጣጣኝ ዋጋ እሰራለወዉ
8 አመት የሥራ ልምድም አለኝ
0993930353

ስለ ስራ!

24 Jan, 09:01


mi chiamo Bin Ali ... አዲስአባ የገባሁት ድሮ ነው በ85 ... ስወለድ 😉
.
... እኩዮቼ በልምድ አዋላጅ 'ወጣ መጣ' ሲባሉ Ospedale ከተወለዱት ጥቂቶች አንዱ ነኝ 😅 ... እስከ 2006 ትምሮ ላይ ነበርኩ ... የማነብርሀን እና SOS ... አየርጤናም 3 ሳምንት ተምሬ ነበር ተማሪና አስተማሪ መለየት ከብዶኝ ወጣሁ እንጂ 😃 ... ድሬዳዋ 3.8 አምጥቼ በማርኬቲንግ መርቀውኛል ... ሰቃይ ነበርኩ

ሽቄም እንደትምሮ የሚቀለኝ መስሎኝ ነበር ... ተቀጥሬ ባለመስራቴ ይቆጨኛል ... ከቅጥር መማር የምችላቸው ብዙ ነገሮች አምልጠውኝ ከኪሳራ ለመማር ተገድጃለው ... ብቻ ከ2007 እስከአሁን ፍጋት ላይ ነኝ ... በሸቀልኩት ሳይሆን በራሕመቱ እየኖርኩ ነው 🙏 ... ባለፉት አስር አመታት ጊዜያዊ ስራ ካገኘሁ ጣ እያረኩ በቋሚነት ግን ሰባት ዘርፎች አገላብጫለው/አገላብጠውኛል 😀 ... ወደ ሶስቱ ዞሬ ላልሸና ተገዝቼ በኪሳራ ወጥቻለው ... ሁለቱን እህል ውሀቸው እስኪያልቅ ሰርቻለው ... አሁን ሁለት ስራዎች ላይ ተፍ ተፍ እያልኩ ነው Bonito Caffe 14 ሰራተኞች ይዞ ይኻድማል አርሒቡ ... Dire Bag /ድሬ ዘንቢል ደሞ በደቂቃ 120 ፍሬ በሚያመርት ማሽን የፌስታል ምትክ የጨርቅ ኪሶችን እያቀረበ ነው ... ጅምላ ስትፈልጉ አጩኹልኝ

ሰሞኑን ኢንሻአላህ በአገልግሎት ዘርፍ ሌላ ሽቄ እጀምራለው ... ጎራ ትላላችሁ 😉 ... ሌሎች ያበሰልኳቸው ቀናቸውን የሚጠብቁ ስራዎችም አሉ ... ያላሰብኳቸው በጌታዬ ችሮታ የሚገጥሙኝም አሉ ... ሁሉም አላህ ያለ ግዜ ይደርሳሉ ... ስራዎቼ የሽርክና ናቸው ... አብሮ መስራት ጥቅሙ ቢያንስም መልካም ጎኑ ሰፊ ነውና ይመቸኛል ... እዚም እዛም የማንቧትረው ለዛ ነው ...
.
ቀደዳ ይመቸኛል ... ስለ ስራ! ላይ ከአድሚኖች አንዱ ነኝ ... ስለሽቄ ቦተሊካ ማህበራዊ ነገር እከትባለው ... እናቆራለው 😎
.
... አባቴ ጀርባና እናቴ ሆድ የኖርኩት ሳይታሰብ 32 አመት ደፍኛለው ... ፈሊላሂልሐምድ ... የሀበሻ ድርሻዬን ይዤ ራሴን በአራት አባዝቻለው ... ቀጣይ እንደመንግስታችን በጎ ፈቃድ ወይ ከኬንያ ወይ ከኡጋንዳ እንወልድ ይሆናል 😊 ... መቼም ይሄን ፊት አረብ አይፈቅደውም 🚶

ስለ ስራ!

18 Jan, 19:50


Live stream finished (2 hours)

ስለ ስራ!

18 Jan, 19:50


ውይይታችን ተጠናቋል!

ስለ ዶሮ እርባታ በዶክተር ሰላሀዲን አሊ የቀረበልን ፕሮግራም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ዶክተር ከተጣበበ ጊዜው ሰውቶ ጥሪያችንን በማክበር ስለ ዶሮ እርባታ መነሻ የሚሆኑ ሀሳቦችን ዳሰሳ አድርጎልናል።

በፕሮግራሙ ዶሮ እርባታን መስራት ለሚፈልጉ ስራው ስላለው እድልና በስራ ሂደት ስለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች ተዘርዝረዋል። የተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎች በዝርዝር ምላሽ ተሰጥተዋል።

በጥያቄያችሁ መሰረት የዶክተርን መገኛ አድራሻ እና የድምፅ ቅጂውን እዚሁ ቴሌግራም ገፅ ላይ የምናያይዝ ይሆናል።

ዶክተርን በሚገባ አመስግኑልን! 👌👍

ስለ ስራ!

18 Jan, 17:48


እንደምን አመሻችሁ ተከታታዮቻችን  . . .

ውይይታችን ተጀምሯል!

ውይይቱን ማስታወሻ በመያዝ በጥሞና እና በአንክሮ እንድትከታተሉ  እንጋብዛለን።

ከርዕሱ ጋር የሚዛመዱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ከስር ባለው ኮሜንት መስጫ ሳጥን ላይ ማስፈር ትችላላችሁ! 👇👇👇

የውይይቱን ሊንክ ለሌሎች ጋብዙ!
https://t.me/selesera?livestream

ስለ ስራ!

18 Jan, 17:40


Live stream started

ስለ ስራ!

18 Jan, 17:40


Live stream scheduled for

ስለ ስራ!

18 Jan, 16:37


ከዶክተር ሰላሀዲን ጋር ስለ ዶሮ እርባታ ያዘጋጀነው ውይይት ሊጀምር አንድ ሰአት ብቻ ይቀረዋል።

ዝግጁ ናችሁ?

ሌሎች ወዳጆችዎን ይጋብዙ  . . .

https://t.me/selesera?livestream

ስለ ስራ!

18 Jan, 12:58


የሁለት አመት ጉዞ - ስለ ስራ!

ፌስቡክ ግሩፕ --------- 118ሺ በላይ
(አንድ መቶ አስራ ስምንት ሺ አባላት)
ፌስቡክ ፔጅ ---------- 1600 +
ቴሌግራም ገፅ ---------- 6600+ አባላት
(https://t.me/selesera

የስለ ስራ! ግሩፕ አድሚኖችን ያውቋቸዋል?
ተወዳጇቸው!

Zubeyda Awol ( @Zubenet
Ezedin Sultan ( @ezedin92
ሉላ ኢሳ ( @Yeamalenat
Mubarek Sadiq ( @Ibnusadik
Ina Omer ( @Inuyaa
Bin Ali ( @wdiali
ስለ ስራ ( @Selesera_bot

ሁለት አመታት ከናንተ ጋር በመዝለቃችን ደስታ ይሰማናል። ዛሬ ምሽት 2:45 በስለ ስራ! ቴሌግራም ገፅ ይጠብቁን።

@ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

18 Jan, 12:16


በነገራችን ላይ ወረዳ ካሉ የከተማ ግብርና ፅህፈት ቤቶች የዶሮ ጫጩቶችን ወስዶ ማሳደግ እና የዶሮ እርባታ መጀመር እንደሚቻል ያውቃሉ?

ከጥቃቅኑ ከዚህ ወረዳ ከሚሰጠው አምስት ፍሬ ጫጩት እስከ ሚሊዮኖች የሚተረፍበት የዶሮ ቢዝነስ ለማውራት ዛሬ ማታ ቀጠሮ ይዘናል።

በጉዳዩ ላይ በቂ የሆነ የትምህርትና የልምድ ዝግጅት ያላቸውን ዶክተር ሰለሀዲንን ስንጋብዝ - ለናንተ ቤተሰቦቻችን በቂ ስንቅ እንደሚያቀርቡልን በመተማመን ነው።

🎊🎊🎊🎉🎉🎉🎊🎊🎊

ባልተያያዘ ግሩፓችን ስለስራ ዛሬ ሁለተኛ አመቱን አጠናቋል። በነዚህ 2 አመታት የሚጠበቅብንን ያህል ባይሆንም የምንችለውን ሁሉ ለቤተሰቦቻችን ለማድረስ የተቻለንን አድርገናል። ለግሩፑ ማደግን ጠቃሚነት የናንተ ቤተሰቦቻችን ሀሳብና ድጋፍ የማይተመን ስንቃችን ነበር - ወደፊትም እንደሚቀጥል ተስፋ እናደርጋለን -

አብራችሁን ስለሆናችሁ - ስለምትሳተፉ - ስለምትታገሱን ጭምር እናመሰግናለን 😍

🎊🎊🎊🎉🎉🎉🎊🎊🎊

ዛሬ ቅዳሜ ማታ ከምሽቱ 2:45 በስለስራ ቴሌግራም ቻናል እንገናኝ ☺️

#ስራ_በእውቀት_እንዲሰራ_እንተጋለን

https://t.me/selesera

@ሉላ ኢሳ

ስለ ስራ!

18 Jan, 12:07


ትጉህ የስራ ሰዎች፣ለውጥ ፈላጊዎች፣በትብብር መስራትን የሚያስተምሩ፣ለመማማርም ለማስተማርም ግንባራቸው የማይታጠፍ ምርጥ እህቶችና ወንድሞችን ከተቀላቀልኩ ሁለት አመት ሆነ !

#ስለስራ ግሩፕ አድሚኖች እንኳን ደስ አላችሁ !

የግሩፑ አባላቶቻችን በቅርቡ የምናስተዋውቃችሁ አዲስ ነገር ይኖረናል አብራችሁን ስለዘለቃችሁ ምስጋናችን የላቀ ነው ! ክበሩልን

እንደተለመደው ዛሬ ማታ የውይይት ሰአታችን ላይ እንጠብቃችኋለን።

✍️ ዙበይዳ አወል

ስለ ስራ!

17 Jan, 06:08


ይህን ጊዜ የምናልፈው በስራና በስራ ብቻ ነው ብለን ገግመናል ☺️

ከስራዎች ደግሞ በሀገራችን ውስጥ በቀላሉ ምርት የሚሰጡ ስራዎች ላይ ብናተኩር ቢያንስ በማዕበሉ ተናውጦ ከመስመጥ ራሳችንን እናድናለን ብለን አምነናል።

የሰው ልጅ ከሚደገፍባቸው፣ ለመኖር ከሚያስፈልጉት የመጨረሻው ትንሹ ነገር ምግብ ነውና ስለማምረት ስናስብ ከምግብ ጀምረናል።

የዶሮ እርባታ ቢዝነስ በእውቀት ካልተሰራ አስቸጋሪ ከሚባሉ ዘርፎች የሚመደብ መሆኑን በተለያየ አጋጣሚ እንሰማለን። ለዚህም ነው በዶሮ እርባታ ላይ የዳበረ ልምድ ያላቸውን ዶክተር ሰላሀዲን አሊን ስለዚህ ሳይንስ እንዲያስረዱን የጠየቅናቸው።

እሳቸውም ጥሪያችንን አክብረው ጉዳዩን ለቤተሰቦቻችንን ለማስረዳት ነገ ቅዳሜ፣ ጥር 10 ከምሽቱ 2:45 ላይ ቀጠሮ የያዝነው።

እና...ም ውይይታችን ላይ ተሳተፉ፣ ይሄን ፖስትም ሼር ኮፒ ሊንክ፣ ዱኤት በማድረግ ለሰዎች አስተላልፉ ☺️

#ስራ_በእውቀት_እንዲሰራ_እንተጋለን

✍️ ሉላ ኢሳ

ስለ ስራ!

17 Jan, 01:25


አዲስ ቢዝነስ መፅሀፍ በገበያ ላይ  . . .

በሀገራችን ቋንቋዎች የተፃፉ የቢዝነስ መፃህፍት በጣም ውስን ናቸው። አብዛኞቹ ንድፈ ሀሳብን የያዙ እንጂ መሬት ላይ ያለውን የሀገራችንን ተጨባጭ የዳሰሱ አይደሉም።

በዚህ ረገድ ከ20 አመት በላይ የቢዝነስና የማማከር ልምድ ባለው ኢንጂነር ከፈለኝ ሀይሉ "ቢዝነስ ሀሁ በኢትዮጵያ፣ ኪሳራም ስራ ነው!" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የቢዝነስ መፅሀፍ ለገበያ ቀርቧል።

ኢንጂነር ከፈለኝ ሀይሉ የቅዳሜ እንግዳችን የነበሩና ግሩፑ ላይ ያለ ቅድመ ፈቃድ ፖስት እንዲያደርጉ ፈቃድ የተሰጣቸው ትጉህ የቢዝነስ መሀፊ ናቸው።

ለጀማሪ ነጋዴዎች ትልቅ ግብአት የሚሆን መፅሀፍ በ"400" ብር ብቻ ።

ከምንም በላይ የቢዝነስና ንግድ ሕጎችን በግልጽ እንድናውቅና ተሻጋሪ ቢዝነስ እንዲኖረን ያግዛል።

ይህ መፅሃፍ የት ይገኛል ? 
(ኮሜንት ላይ ይመልከቱ👇

ስለ ስራ!

16 Jan, 17:35


#10 #ቀናት #ቀሩት

አሁንም አባላት የዲስካውንት ዕድሉን እየተጠቀሙበት ነው !!!

እርስዎስ?

ለ"ስለ ስራ!" ግሩፕ አባላት የተሰጠው 10% የጥርስ ህክምና ዲስካውንት ማብቂያ ጊዜው ጥር 18 /2017 ነው።

0973090909 ላይ ፈጥነው ይደውሉ። አሁኑኑ ቀጠሮ ያስይዙ።

የፖስቱን ስክሪን ሹት መያዝ በቂ ነው

Dr Temam Dental Clinic

አዲስ አበባ መርካቶ ሲኒማራስ ፊትለፊት፣ ኡራጎ የገበያ ማዕከል 5ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን።

ፍላጎታችን ፈገግታዎ ነው!

Our Concern Is Your Smile.

ስለ ስራ!

16 Jan, 06:12


ውይይታችን እንደቀጠለ ነው!

ያለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ስለ ምርትና ምርታማነት ዳሰሳ አድርገናል። በቀጣይ ሳምንታት ደግሞ ቀጥታ ምን እናምርት? በሚል ርዕስ ዝርዝር ሀሳቦችን እየዳሰስን እንሰነብታለን።

የፊታችን ቅዳሜ ጥር 10 ምሸት ስለ ዶሮ እርባታ እናወጋለን። ከዶሮ እርባታ ጋር የተያያዙ ርዕሰ ጉዳዮች ሰአት በፈቀደ ያህል ለማቅረብ እንሞክራለን።

የኢትዮ ዶሮ እርባታና ማቀነባበርያ ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሰላሀዲን አሊን ጋብዘናል። ዶክተር ሰላሀዲን ከ1200 በላይ ሰዎችን በዶሮ እርባታና መኖ ማቀነባበር ላይ ስልጠና ሰጥተዋል።

ቅዳሜ ጥር 10/2017 ምሽት 2:45 ላይ በሚኖረን ፕሮግራም ፈቃደኛ ሆነው ያላቸውን እውቀትና ልምድ ለማካፈል ቀጠሮ ይዘናል። ከናንተ የሚጠበቀው በጊዜው ተገኝታችን ፕሮግራሙን መከታተልና ያሏችሁን ጥያቄዎች ማቅረብ ነው።

ከ6550 በላይ ተከታይ ያለውን የስለ ስራ! ቴሌግራም ቻናል ይቀላቀሉ!
https://t.me/selesera

@ስለ ስራ! ስራ በእውቀት እንዲሰራ እንተጋለን!

ስለ ስራ!

15 Jan, 15:48


የድምፅ ቅጂውን እነሆ!

ቅዳሜ ጥር 03/2017 ምሽት ስድስተኛ ምዕራፍ አንደኛ መሰናዶ ማድረጋችን ይታወሳል።

ውይይቱ እንግዳ አድርጎ የጋበዘው ዶክተር አብዱልቃድር ወሀብን ነበር። ምርትና ምርታማነት በሚል ርዕስ በጋዜጠኛ ዙበይዳ አወል አወያይነት የቀረበው ፕሮግራም በተሳታፊዎች ዘንድ መወደዱ ከተሰጡን አስተያየቶች ለመረዳት ችለናል።

የውይይቱ አቅራቢ ዶክተር አብዱልቃድር በዘርፉ ካላቸው በቂ የትምህርት ዝግጅትና ከፍተኛ ልምድ በመነሳት መሳጭና ተጨባጭን እንድንመለከት ያደረገ ገለፃ አድርገዋል። ከተሳታፊዎች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች በቂ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቅራቢያችንን ዶክተር አብዱልቃድር ከተጣበበ ጊዜያቸው ቀንሰው ጥሪያችንን አክብረው ስለተገኙልን በግሩፑ ስም እያመሰገንን በዕለቱ የተደረገውን ውይይት የድምፅ ቅጂ በቴሌግራም ገፃችን አያይዘነዋል።
https://t.me/selesera

በዚህም ሳምንት በሌላ እንግዳና ርዕስ ውይይታችን ይቀጥላል።

@ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

14 Jan, 05:25


#13 #ቀናት #ቀሩት

ለ"ስለ ስራ" ግሩፕ አባላት የተሰጠው 10% የጥርስ ህክምና ዲስካውንት ማብቂያ ጊዜው ጥር 18 /2017 መሆኑን አይርሱ

0973090909
ፈጥነው ይደውሉ አሁኑኑ ቀጠሮ ያስይዙ

የፖስቱን ስክሪን ሹት መያዝ በቂ ነው

Dr Temam Dental Clinic

አዲስ አበባ መርካቶ ሲኒማራስ ፊትለፊት ኡራጎ የገበያ ማዕከል 5ኛ ፎቅ ላይ እንገኛለን

ፍላጎታችን ፈገግታዎ ነው

ስለ ስራ!

13 Jan, 15:15


የስለ ስራ! ግሩፕ አድሚኖችን ያውቋቸዋል?
ተወዳጇቸው!

Zubeyda Awol ( @Zubenet
Ezedin Sultan ( @ezedin92
ሉላ ኢሳ ( @Yeamalenat
Mubarek Sadiq ( @Ibnusadik
Ina Omer ( @Inuyaa
Bin Ali ( @wdiali
ስለ ስራ ( @Selesera_bot

ፖስቶቻችሁን ፈትሾ አፕሩቭ ማድረግ፣ የተለያዩ ጠቃሚ መረጃዎች አዘጋጅቶ መፖሰት፣ ውይይት አቅራቢና ርዕስ በመምረጥ ውይይቶችን ማሰናዳት ከብዙ በጥቂቱ በአድሚኖች አማካኝነት የሚሰሩ ስራዎች ናቸው።

ግሩፑን የተመለከቱ ሀሳብና አስተያየታችሁን በተመቻችሁ ጊዜ ለቀረባችሁ የአድሚን አባላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

@ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

13 Jan, 08:47


የሰነደ-ሙዓለ ንዋዮች ገበያ (Capital Market) መጀመሩን ሰምታችኋል። እናም በገበያው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳታፊ ለምትሆኑ ወዳጆች በሶስት ርዕሰ - ጉዳዮች ማለትም:-

1. የጋራ ኢንቨስትመንት ፈንዶች (collective investment schemes)
2. የፋይናንስ ገበያ ኤቲክስ (Ethics in Financial Market) እንዲሁም
3. ከሸሪዓ ተስማሚ የካፒታል ገበያ (Sharia-Compliant Capital Market)

በተመለከተ በጣም አጠር አድርጌ ያዘጋጀኋቸውን ሞጁሎች እንድታነቡ ተጋብዛችኋል። ጥያቄዎቹንም እየሠራችሁ ራሳችሁን ገምግሙበት።

PDF ኡን አውርዳችሁ ማንበብ ትችላላችሁ። ለዛሬ ተ.ቁ. 1 ተቀምጧል።

መልካም ንባብ!

በዶክተር ሀውለት አህመድ

ስለ ስራ!

11 Jan, 17:40


Live stream scheduled for

ስለ ስራ!

10 Jan, 19:05


የስለ ስራ! ማህበራዊ ድረ-ገፅ አማራጮችን በመቀላቀልና ለሌሎች በማጋራት ተደራሽነቱን ያስፉ!

👉 FB - Group  https://www.facebook.com/groups/1153093882014917/?ref=share&mibextid=NSMWBT

👉 FB - Page
https://www.facebook.com/profile.php?id=61552032783167&mibextid=ZbWKwL

👉 Youtube - https://www.youtube.com/@SilSira-zs5rw

👉 Tiktok - tiktok.com/@sile.sira

👉 WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029Va5Ch0O9WtBw5eGcdZ3H

👉 Telegram
https://t.me/selesera

ስለ ትብብራችሁ እናመሰግናለን!

ስለ ስራ!

10 Jan, 11:56


ነገ ቅዳሜ ጥር 03 ምሽት 2:45 ላይ በዚሁ ቴሌግራም ቻናላችን ላይ በቀጥታ ስርጭት ከ ዶክተር አብዱልቃድር ወሀብ ጋር ስለ ምርትና ምርታማነት የሚኖረንን ወይይት ለመከታተል ዝግጁ ናችሁ?

🖐🤚

ስለ ስራ!

10 Jan, 01:34


በቅናሹ እየተጠቀሙ ነውን?

ዶክተር ተማም የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ለ ስለ ስራ! ግሩፕ አባላት ለአንድ ወር የሚቆይ የ10% ቅናሽ አድርገዋል።

የትኛውንም አገልግሎት ሲጠቀሙ ይህንን ፖስት እስክሪን-ሹት ብቻ በማሳየት የቅናሹ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ።

ልቁ ቅናሹ ከታህሳስ 18- ጥር 18 ድረስ ይቆያል!

አድራሻ ሲኒማ ራስ ፊትለፊት፣ ኡራጎ ህንፃ 5ኛ ፎቅ
ለበለጠ መረጃ፦ 0973090909

ዶክተር ተማም የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ለግሩፓችን አባላት ለሰጠው ልዩ ቅናሽ እናመሰግናለን!

Dr. Temam Dental Clinic

ስለ ስራ!

09 Jan, 09:19


ውድ የስለ ስራ! ቤተሰቦቻችን

አስተማሪው የቅዳሜ ምሽት መሰናዷችን ስድስተኛ ምዕራፍ የፊታችን ቅዳሜ ይጀምራል።

በስድስተኛ ምዕራፍ ፕሮግራሞቻችን ዝርዝር የስራ መስኮችን በየዘርፉ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን በመጋበዝ እናቀርባለን።

ምን ልስራ? ብለው ለተጨነቁ የተለያዩ አማራጭ የስራ ሀሳቦችን እንዳስሳለን

ቅዳሜ ጥር 03/2017 ምሽት 2:45 ላይ ስለ ምርትና ምርታማነት ለማውራት በዘርፉ አንቱታን ያተረፉና ሰፊ ልምድ ያላቸውን ዶክተር አብዱልቃድር ወሀብ ጋብዘናል።

ይህ ውይይት ቀጣይ ለሚኖሩን ዝርዝር የስራ ሀሳቦች ዳሰሳ ወሳኝ ርዕስ ስለሆነ ሁላችሁም እንድትከታተሉ ጋብዘናል።

@ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን

ስለ ስራ!

07 Jan, 16:58


ስድስተኛ ምዕራፍ ፣ አንደኛ ሳምንት መሰናዶ
የፊታችን ቅዳሜ . . .

ስለ ስራ!

03 Jan, 16:29


#የቢሮ_ሰራተኞች_ጤና_ጉዳይ
- - - - - - - - - - - - -
በፊዚክስ ህግ ዎርክ (ስራ) እኩል ይሆናል ፎርስ (ሃይል) ሲባዛ ዲስታንስ (ርቀት) ነው፡፡ በዚህ ህግ መሰረት በርካታ የቢሮ ሰራተኞች ስራ እየሰራን አይደለም ማለት ነው (ኧረ አትቀልድ በለኛ😁)፡፡የተወሰነ እውነት አለው የፊዚክሱ ህግ፡፡የፊዚክሱን አይነት ስራ የሚሰሩት ሰዎች ይበልጥ ጤነኛ ሆነው እናገኛቸዋለን፡፡

ለማንኛውም ይህንን የፊዚክሱን አይነት ስራ የማንሰራ የቢሮ ውስጥ ሰራተኞች ጤናችንን ለመጠበቅ የሚከተሉትን 9 ምክረ ሃሳቦች መተግበር ያስፈልጋል፡፡

1. ንቁ ይሁኑ (Stay Active)፡- በየ ግማሽ ሰዓቱ ወይም በየአንድ ሰዓቱ ከተቀመጥንበት መነሳት እና ዞር ዞር ማለት እና ሰውነታችንን ማፍታት ያስፈልጋል፡፡ አለበለዚያም እዛው በተቀመጥንበት ሰውነታችንን ማፍታት አስፈላጊ ነው፡፡ ይህንን ማድረጋችን ወገብ እና አንገታችን እንዳይታመም ይረዳል፡፡

2. መልካም አቀማመጥ ይቀመጡ (Maintain Good Posture)፡- ወንበራችንን በሚመች መልኩ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ሲቀመጡ ጉልበትዎ በ90 ዲግሪ እንዲሆን ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ኮምፒውተራችን በአይናችን ትዩዩ መሆኑን ማረጋገጥ ያስፈልጋል፡፡የእግራችን ጫማ ደግሞ ወለሉ ላይ ሙሉ በሙሉ እንዲያርፍ ይሁን፡፡ሲቀመጡ ወገብዎት ከወንበሩ ጋር ግጥምጥም እንዲል እና ቀጥ እንዲል ያድርጉ፡፡

3. ውሃ ይጠጡ (Hydrate)፡-ውሃ ቀኑን ሙሉ ይጠጡ፡፡ ጣፋጭ እና ስኳር የበዛባቸው መጠጦችን አያብዙ፡፡ቡና አይብዛ እንጂ ጥሩ ነው፡፡

4. ጤናማ ቁርሶችን ይመገቡ (Eat Healthy Snacks and Meals)፡- ፍራፍሬ፣ ለውዝ፣ አትክልት መመገብ አሪፍ ነገር ነው፡፡ስኳራማ ነገሮችን አያዘውትሩ፡፡

5. የጸሐይ እረፍት ይውሰዱ (Get Fresh Air and Sunlight)፡ ንጹህ አየር እና የፀሐይ ብርሃን ለማግኘት በአገኙት አጋጣሚ ሁሉ ጥረት ያድርጉ፡፡ ይህም የቪታሚን ዲ መጠንዎ አንዲስተካከል እና በሽታ የመከላከል አቅምዎ እና አጥንትዎ እንዲጠነክር ይረዳል፡፡

6. ጭንቀትን ያስተንፍሱ (Manage Stress)፡- የተለያዩ ጭንቀትን ወይም ስነ ልቦናዊ ጫናዎችን ለመቀነስ የሚረዱ ስልቶችን ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡

7. ምቹ የቢሮ እቃዎችን ይጠቀሙ (Use Healthy Office Equipment)፡- ለምሳሌ ለመቀመጫ የማይቆረቁር እና ድጋፍ ያለቸውን ወንበሮች ይጠቀሙ፡፡

8. በቂ እና ሰላማዊ እንቅልፍ ያግኙ (Good Sleep Hygiene)፡-ማታ ላይ በቂ እንቅልፍ ማግኘት ያስፈልጋል፡፡ እንቅልፍ ማጣት ቀናችን ጥሩ እንዳይሆን ያደርጋል፡፡ለዚህ ይረዳ ዘንድ ተመሳሳይ የመተኛ እና የመነሻ ሰዓትን ልምድ ማድረግ እጅግ ጠቃሚ ነው፡፡

9. ከስራ ባልደረባዎችዎ ጋር ጥሩ ተግባቦት መፍጠር (Connect with Colleagues) ፡- መልካም የስራ ባልደረባ ጋር ትግባቦት ቀናችን ጥሩ እንዲሆን እና ጤናማ እንሆን ዘንድ ይረዳ ነበር፡፡

ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራት በመከወን የቢሮ ሰራተኞች ጤናችንን ለመጠበቅ ይረዳናል፡፡

'ላይክ እና ሼር በታደርጉም፤ ሃሳብ ጥያቄም ካለ ኮሜንት ብትጽፉ መልዕክቱ ለብዙዎች ይደርስ ዘንድ ይረዳል'
ዶ/ር Umer Al Pawe

ስለ ስራ!

03 Jan, 07:31


#ጥቆማ

በአዲስ አበባና አካባቢዋ የሚኖሩና የ " 5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢንሼቲቪ " ስልጠናዎችን ለመሰልጠን ላሰቡ ጥሩ እድል መመቻቸቱን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) አሳውቋል።

ስልጠናዎቹን ለመውሰድ ለሚመጡ ሰልጣኞች የኮምፒውተር እና ኢንተርኔት አቅርቦት ዝግጁ መደረጉ ተጠቁሟል።

የዚህ እድል ተጠቃሚ ለመሆን የሚፈልጉ እንዲመዘገቡም ጥሪ ቀርቧል።

የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፣ የመንግስትና የግል ሰራተኞች፣ በአጠቃላይ ሁሉም ዜጎች የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ኢንሼቲቪ ስልጠናዎችን መሰልጠን ይችላሉ ተብሏል።

ስልጠናው ከጥር 3/2017 ዓ.ም ጀምሮ ሁልጊዜ በሳምንቱ የእረፍት ቀናት (ቅዳሜና እሁድ) እንደሚሰጥ ተገልጿል።

የስልጠና ቀናት
#ቅዳሜ እና #እሁድ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ አመሻሽ 11:30 እንደሆነ ተመላክቷል።

የስልጠና ቦታው አዲስ አበባ ወሎ ሰፈር አካባቢ በሚገኘው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ቢሮ ሲሆን ለመመዝገብ ይህን ሊንክ 
https://awareness.insa.gov.et/index.php/143154?lang=am መጠቀም ይቻላል ተብሏል።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

02 Jan, 13:39


እቃ ሳይረከቡ ብር አይክፈሉ . . .

ስለ ስራ! ግሩፓችን በፌስቡክ ከ114 ሺ በላይ አባላትን ይዟል። በቀን ውስጥ በመቶዎች የሚቆጠሩ ከስራ ጋር ተዛማጅ የሆኑ ፖስቶች በግሩፑ ይለቀቃሉ። ከጠቅላላ አባላቱ ከ80% በላይ የሚሆኑት ንቁ ተሳታፊዎች ናቸው።

ለሁሉም ክፍት የሆነ ማህበራዊ መገናኛ ስለሆነ በተቻለ መጠን የሚቀርቡ ማስታወቂያዎችን ትክክለኝነት በማረጋገጥ ግብይት መፈፀም የገዢው ሀላፊነት ነው።

አንዳንድ አካላት አካውንት በመቀያየር ሆን ብለው እጃቸው ላይ የማይገኝ እቃን በመለጠፍና ቀብድ በመቀበል እያጭበረበሩ እንደሚገኙ ጥቆማ ደርሶናል። እነኚህ አባላት ላይ ከግሩፑ የማስወገድ ስራ ሰርተናል።

ሆኖም የትኛውም አባል ግሩፑ ላይ የተለቀቁ ማስታወቂያዎችን ብቻ በመመልከት ክፍያ እንዳይፈፅም እናሳስባለን። ይልቅ ማስታወቂያው ላይ የተለቀቀው እቃ በሚፈልገው መልኩ መሆኑን አረጋግጦ ሲቀበል ብቻ ግዢ መፈፀም ይኖርበታል።

መሰል የማጭበርበር ድርጊቶች ላይ የተሰማሩ ሰዎችን ብትጠቁሙንና report ብታደርጉ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ከግሩፑ የምናሰናብት ይሆናል።

ስለ ስራ! ከሁላችን ለሁላችን!

ስለ ስራ!

02 Jan, 10:37


#እንድታውቁት

" 12 ሺ ለሚሆኑ ግብር ከፋዮች የታክስ መክፈያ ማዕከል ቅያሪ ተደርጓል " - የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ

የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥን ተደራሽ ለማድረግ እና ካለው የተገልጋይ ብዛት አኳያ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸግር በመሆኑ ለ12 ሺህ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ክፍያ ማዕከል (Tax Center) ቦታ ቅያሪ ማድረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የቢሮው የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ " የቦታ ቅያሪው የተደረገው በቦታው የበርካታ ግብር ከፋዮች ጫና በመኖሩ የተወሰነውን በመቀነስ ግብር ከፋዩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚችልበትን እድል ለመፍጠር ነው " ብለዋል።

ቅያሪው የተደረገው ከስታዲየም አካባቢ የሃ ህንፃ ወደ ጉርድ ሾላ ከሳሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ወደሚገኘው ሜሪዲያን ኮንቬሽን ሴንተር ነው።

በአዲስ አበባ 11 የአንስተኛ ፣ 5 የመካከለኛ እና 1 የከፍተኛ ግብር ከፋይ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የሚገኙ ሲሆኑ የአሁኑ 17ኛው ቅርንጫፍ ነው ተብሏል።

የቦታ ቅያሪው የሚመለከታቸው ተገልጋዮች ስማቸውን ከላይ በተያያዘው ፋይል በመመልከት ከጥር 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

01 Jan, 19:06


#እንድታውቁት

አዲስ አበባ ውስጥ አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ይዞ መገኘት አስገዳጅ ሆኗል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ከዛሬ ታህሳስ 23 , 2017 ዓ.ም (Jan 1st 2025) ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሆኗል።

በሌላ ተያያዥ መረጃ ...

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ " ፋይዳን ለባንክ አገልግሎት አስገዳጅነት " ትዕዛዝ ወደ ትግበራ መግባት ተከትሎ የተለያዩ ባንኮች የማርኬቲንግ እና ኮርፖሬት ህዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ሀላፊዎች ያሳተፈ በጥምረት ግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አሳውቆናል።

ከኃላፊዎች ጋር በነበረ ውይይት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ ፤ " የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ባንኮች በፋይዳ መታወቂያ ዙሪያ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን ልክ እንደ አንድ የባንክ አገልግሎት አጽንዖት ተሰጥቶት እንዲሰሩ " ሲሉ አሳስበዋል።

#ፋይዳለኢትዮጵያ #መታወቅ #አካታች #DigitalID

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

29 Dec, 08:33


በቅናሹ ይጠቀሙ

ዶክተር ተማም የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ለ ስለ ስራ! ግሩፕ አባላት ለአንድ ወር የሚቆይ የ10% ቅናሽ አድርገዋል።

የትኛውንም አገልግሎት ሲጠቀሙ ይህንን ፖስት እስክሪን-ሹት ብቻ በማሳየት የቅናሹ ተጠቃሚ መሆን ይችላሉ።

ልቁ ቅናሹ ከታህሳስ 18- ጥር 18 ድረስ ይቆያል!

አድራሻ ሲኒማ ራስ ፊትለፊት፣ ኡራጎ ህንፃ 5ኛ ፎቅ
ለበለጠ መረጃ፦ 0973090909

ዶክተር ተማም የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ለግሩፓችን አባላት ለሰጠው ልዩ ቅናሽ እናመሰግናለን!

Dr. Temam Dental Clinic

ስለ ስራ!

29 Dec, 06:41


የስለ ስራ! ማህበራዊ ድረ-ገፅ አማራጮችን በመቀላቀልና ለሌሎች በማጋራት ተደራሽነቱን ያስፉ!

👉 FB - Group  https://www.facebook.com/groups/1153093882014917/?ref=share&mibextid=NSMWBT

👉 FB - Page
https://www.facebook.com/profile.php?id=61552032783167&mibextid=ZbWKwL

👉 Youtube - https://www.youtube.com/@SilSira-zs5rw

👉 Tiktok - tiktok.com/@sile.sira

👉 WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029Va5Ch0O9WtBw5eGcdZ3H

👉 Telegram
https://t.me/selesera

ስለ ትብብራችሁ እናመሰግናለን!

ስለ ስራ!

28 Dec, 05:25


አዲስ ቢዝነስ መፅሀፍ በገበያ ላይ . . .

በሀገራችን ቋንቋዎች የተፃፉ የቢዝነስ መፃህፍት በጣም ውስን ናቸው። አብዛኞቹ ንድፈ ሀሳብን የያዙ እንጂ መሬት ላይ ያለውን የሀገራችንን ተጨባጭ የዳሰሱ አይደሉም።

በዚህ ረገድ ከ20 አመት በላይ የቢዝነስና የማማከር ልምድ ባለው ኢንጂነር ከፈለኝ ሀይሉ "ቢዝነስ ሀሁ በኢትዮጵያ፣ ኪሳራም ስራ ነው!" በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የቢዝነስ መፅሀፍ ለገበያ ቀርቧል።

ኢንጂነር ከፈለኝ ሀይሉ የቅዳሜ እንግዳችን የነበሩና ግሩፑ ላይ ያለ ቅድመ ፈቃድ ፖስት እንዲያደርጉ ፈቃድ የተሰጣቸው ትጉህ የቢዝነስ መሀፊ ናቸው።

ለጀማሪ ነጋዴዎች ትልቅ ግብአት የሚሆን መፅሀፍ በ"400" ብር ብቻ ።

ከምንም በላይ የቢዝነስና ንግድ ሕጎችን በግልጽ እንድናውቅና ተሻጋሪ ቢዝነስ እንዲኖረን ያግዛል።

ይህ መፅሃፍ የት ይገኛል ?

👉1ኛ አሪፍ መፃህፍት መደብር አራት ኪሎ አብርሆት ቤተመፃህፍት አጠገብ ስልክ
+251913057242 ወይም +251951106930
👉ኢቲኬር ዋና መስሪያ ቤት 22 ጎላጉል አደባባይ ፊትለፊት ህንፃ ሁለተኛ ፎቅ ላይ የኢቲኬር ብድርና ቁጠባ ፅ/ቤት ።
👉ጀርመን አደባባይ ግርማ ህንፃ አዩ ሱፐር ማርኬት መግቢያ አጠገብ ላይ ባለ መደብር
ስልክ +251922842053
👉ለገሃር መድኃኔዓለም ቤተክርስትያን አጠገብ ኢቦኒ ካፌ
👉 ፒያሳ አብዱ ቡክ ዴሊቨሪ

ስለ ስራ!

09 Dec, 14:52


🌟ውድ የስለ ስራ! ቤተሰቦች እንደምን ሰነበታችሁ💫

ቃል በገባነው መሰረት ፖስቶቻቸው ያለ ፈቃድ ስለ ስራ! ግሩፕ ላይ ቢለቀቅ ለናንተ ጠቃሚ ይሆናል ያልናቸው አምስት ፀሀፊያንን ልየታ አድርገናል።
1. ኢንጂነር ከፈለኝ ሀይሉ (የቅዳሜ እንግዳችን የነበሩ)
2. ዶክተር ሀውለት አህመድ (Phd)
3. አቶ ኢብራሂም አብዱ (የቅዳሜ እንግዳችን የነበሩ)
4. ኢንጂነር ጌቱ ከበደ
5. ኢንጂነር ቢጃይ ናይከር(የቅዳሜ እንግዳችን የነበሩ)

እዚሁ መንደር ለረጅም ጊዜያት የስራውን ማህበረሰብ ግንዛቤ ለማስፋት ከፍተኛ ጥረት ያደረጉ ባለሙያዎች ናቸው። እኛም ከእውቀታቸው እንድትጠቀሙ ከዛሬ ህዳር 30 ጀምሮ የpre-approval ፈቃድ ሰጥተናል።

ወደፊት በተለያዩ ዘርፎች የግሩፑን አባል ይጠቅማሉ ለምንላቸው ባለሙያዎች እና ታማኝ online ነጋዴዎች ተመሳሳይ ፈቃድ እንደምንሰጥ እናሳውቃለን።

ስለ ስራ! ስራ በእውቀት እንዲሰራ እንተጋለን!

ስለ ስራ!

08 Dec, 07:32


ውድ የስለ ስራ! ቤተሰቦች - እንደምን አደራችሁ ☀️

በቃላችን መሰረት ሀሳቦቻቸው፣ ትንተናዎቻቸው ለናንተ ይጠቅማል ብለን ላሰብናቸው እዚሁ መንደር ለሚገኙ አምስት ፀሀፊያን የ pre-Approval ፍቃድ ለመስጠት ልየታ አድርገናል።

ነገ ሰኞ 30/2017 እናሳውቃቹሀለን!

እነማን ይሆኑ?!

@ስለ ስራ! ስራ በእውቀት እንዲሰራ እንተጋለን!

ስለ ስራ!

07 Dec, 16:56


የስለ ስራ! ማህበራዊ ድረ-ገፅ አማራጮችን በመቀላቀልና ለሌሎች በማጋራት ተደራሽነቱን ያስፉ!

👉 FB - Group  https://www.facebook.com/groups/1153093882014917/?ref=share&mibextid=NSMWBT

👉 FB - Page
https://www.facebook.com/profile.php?id=61552032783167&mibextid=ZbWKwL

👉 Youtube - https://www.youtube.com/@SilSira-zs5rw

👉 Tiktok - tiktok.com/@sile.sira

👉 WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029Va5Ch0O9WtBw5eGcdZ3H

👉 Telegram
https://t.me/selesera

ስለ ትብብራችሁ እናመሰግናለን!

ስለ ስራ!

06 Dec, 06:03


ስለ ስራ! ግሩፕ የተቋቋመው ሰዎች ስለ ስራ ማውራት፣ መወያየት፣ በቅንነት ሀሳብና መንገድ መጠቋቆምን ባህላቸው እንዲያደርጉ ታስቦ ነው ☺️

ነገር ግን በተደጋጋሚ አባሎቻችን ልጥፋችን እያለፈልን አይደለም ብለው ሲወቅሱን ይስተዋላል።

ምን ምን አይነት ልጥፎች ስለ ስራ ግሩፕ ላይ አያልፉም?

ከፌስቡክ ማርኬት ፕሌስ ቀጥታ ሼር የሚደረጉ የገበያ ማስታወቅያዎች
በቀን ውስጥ ከአንድ በላይ የንግድ ፍላጎት ማስታወቂያዎች
የሀገሪቱን ህግ የሚፃረሩ ማንኛውም አይነት ንግዶች
አስተማማኝነታቸው ያልተረጋገጠ ለጤና እክል ሊሆኑ የሚችሉ የህክምና ማስታወቅያዎች
ባህላዊና ሀይማኖታዊ ቀኖናዎችን የሚጥሱ ማንኛውም አገላለፆች(ፎቶና ፅሁፍ)
የእርዳታ ተማፅኖዎች
ሌሎች ተፎካከሪዎችን የሚያሳንስ ይዘት ያላቸው ማስታወቅያዎች
ፖለቲካዊ እንድምታ ያላቸው ፅሁፎች
የመሳሰሉት

×✖️አያልፉም✖️×

💚በስራና ንግድ ጉዳይ ላይ ምክሮች፣ የአካሄድ ጥቆማዎች የንግድ ህግ ማብራርያዎች
💚ምርትና ምርታማነት ላይ የሚያተኩሩ ስራዎች ማስተዋወቅ
💚የሸማቹን ማህበረሰብ ህይወት ሊያቀሉ የሚችሉ ጥቆማዎች
💚ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቅያዎች

👍ይበረታታሉ

ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

05 Dec, 08:09


ሰላም የስለ ስራ! ገፅ ቤተሰቦቻችን

ስለ ስራ! ስራን የተመለከቱ ጉዳዮች በስፋት የሚቃኝበት ገፅ መሆኑ ይታወቃል። ገፁ የተቋቋመለትን አላማ ከግብ እንዲመታ ፖስቶች ቀድመው ታይተው አፕሩቭ የሚደረጉበትን አሰራር እየተከተልን እንገኛለን።

በንግድ እንቅስቃሴያቸው አመኔታን ላተረፉ፣ ዘውትር ማህበረሰቡን ስለ ስራ የማንቃትና ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ለሚሰሩ እኛው ግሩፕ ላይ ለሚገኙ ለተመረጡ ሰዎች እንደ ጅማሮ ለማበረታታት ያህል pre approval ፈቃድ ልንሰጥ አስበናል።

የዚህ እድል ተጠቃሚ የሆኑ ግለሰቦች ያለምንም ከልካይና የቆይታ ጊዜ በመረጡት ሰአት የግሩፑን ደንቦች የተከተሉ ፖስቶችን መልቀቅ ይችላሉ።

የዚህ እድል ተጠቃሚ ማን ቢሆን የበለጠ የግሩፑን አባላት መጥቀም ይችላሉ ብለው ያስባሉ?

ጥቆማዎችን ኮሜንት ገፅ ላይ ያስፍሩልን፣ እናመሰግናለን!

ስለ ስራ!

05 Dec, 03:01


የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት
ግብይትና ግመታ ረቂቅ አዋጅ አጭር ማብራሪያ

ስለ ስራ!

04 Dec, 16:41


#EthiopianInvestmentHoldings

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፕን ጨምሮ 8 ተቋማት ከአሁን በኃላ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እንደሚተዳደሩ ተነገር።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ 8 ተጨማሪ የመንግስት ድርጅቶችን በስሩ በማካተት ፖርትፎሊዮውን ማስፋቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (ኢኢሆ) በስሩ ከሚገኘትና ከሚያስተዳድራቸው የመንግስት የልማት ድርጅቶች በተጨማሪ 8 አዳዲስ ቁልፍ ተቋማትን በስሩ በማካተት የድርጅቶቹን ቁጥር ጨምሯል።

8ቱ ተቋማት እነማን ናቸው ?

- ኢትዮ ፖስት፣
- ኢትዮ ኢንጂነሪንግ ግሩፐ
- የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት፣
- የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን፣
- የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን፣
- የኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣
- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ኮርፖሬሽን እና ለኢትዮ ፋርማ ግሩT ተጠሪ የሆኑት ብሔራዊ የእንስሳት ጤና ጥቢታ ተቋምና ሺልድ ቫክስ ናቸው።

እነዚህ ቀደም ሲል ለመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታ እና አስተዳደር ተጠሪ የነበሩት የልማት ድርጅቶች ከአሁን ጀምሮ በባለቤትነት የሚተዳደሩትና የሚመሩት በኢኢሆ ስር ሆኗል።

(ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

04 Dec, 07:02


🖐️💫 ሰላም የስለ ስራ! ግሩፕ ቤተሰቦች🌟👋

በብዛት ፖስቶቻችሁ ውድቅ(decline) የሚሆኑት በምን ምክንያት እንደሆነ ያውቃሉ?

ዋነኛው ምክንያት በቀጥታ ወደ ግሩፑ ከመፖሰት ይልቅ ከሌላ ቦታ share የተደረጉ ሲሆኑ ውድቅ ይደረጋሉ። እንዲሁም ማርኬት ፕሌስ ላይ የተጋሩ ፖስቶች ተቀባይነት አይኖራቸውም።

እዚህ ግሩፕ ላይ የሚለቀቁ ፖስቶች ፖስት አድራጊው አስቦበትና ሀላፊነት ወስዶ እንዲሆን ስለሚፈለግ ከላይ በተገለፀው መልኩ የሚደረጉ ፖስቶች እንደማያልፉ በመገንዘብ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደርጉ ለማስታወስ እንወዳለን።

የስለ ስራ! ቴሌግራም ገፅ ይቀላቀሉ
https://t.me/selesera

@ስለ ስራ!
የሁላችን ከሁላችን

ስለ ስራ!

03 Dec, 14:10


ንግድ እና ቀጣናዊ ትስድር ሚኒስቴር "የምርት ነፃ ዝውውርን የሚገድቡ" ያላቸው 283 ሕገ ወጥ የከተማ በር ወይም መቅረጫ ኬላዎች በመላው ሀገሪቱ መኖራቸውን ገለፀ።
ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ ዛሬ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሲሰጡ እንዳሉት ይህ ለምርቶች ዋጋ መጋነን እና የሸቀጦች ዋጋ መናር ምክንያት ሆኗል።
ሚኒስትሩ መሥሪያ ቤታቸው ባለፉት አምስት ወራት በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ የንግድ ተቋማት ላይ እርምጃ ተወስዷል ቢሉም ከምክር ቤት አባላት እርምጃ ለምን እንደተወሰደ? ያ በመሆኑ ምን ውጤት እንደተገኘ እንደማይገለጽ ተጠቅሶ ሚኒስቴሩ ከደላላ ዕጅ አስወጥቶ የሀገሪቱን ንግድ በአግባቡ እየመራ ስለመሆኑ አለመሆኑ ጥያቄ ተነስቶበታል።
የሀገሪቱ ንግድ በደላላ እየተመራ ነው በሚል የቀረበባቸውን ትችት ያጣጣሉት ሚኒስትሩ እውነታው በዚያ ደረጃ የሚገለጽ እንዳልሆነ፣ ሆኖም ግን የደላላ ጣልቃ ገብነት አሁንም የሚቀር እንዳልሆነ ጠቅሰዋል። በየክልሉ በከተሞች መግቢያ እና መመውጫ በር ላይ ገመድ ወጥረው ነጋዴውን ለድርብርብ ክፍያ እና ወጪ የሚዳርጉ ሕገ-ወጥ አሠራሮች በቀላል የማይታይ አደጋ መደቀናቸውን ግን በዚሁ ጊዜ ጠቅሰዋል ሲል ስብሰባውን የተከታተለው የአዲስ አበባው ወኪላችን ሰሎሞን ሙጬ ዘግቧል።

ዜናው ባለቤትነቱ የ DW Amharic ነው

ስለ ስራ!

03 Dec, 13:52


በስለ ስራ! የቴሌግራም ገፅ ምን ሊያገኙ ይችላሉ?
https://t.me/selesera

👉 የቢዝነስ መረጃዎች
👉 ጠቃሚ ውይይቶች
👉 ቢዝነስ ነክ የመፅሀፍት ጥቆማዎች
👉 ስለ ስራ! ግሩፕን የተመለከቱ ጉዳዮች
👉 የስራ ማስታወቂያዎች
👉 የምንዛሬ መረጃዎች
👉 የተለያዩ መመሪያዎችና ፖሊሲዎች  . . .

እነኚህን ሌሎች ከቢዝነስ ጋር የተገናኙ ጉዳዮች በስፋት ይቀርቡበታል።
       
        ይወዳጁ፣ ወዳጆችዎንም ይጋብዙ!

ስለ ስራ!

03 Dec, 09:15


የሲሚንቶ ዋጋ በሲሚንቶ አምራች ፋብሪካዎች እንዲወሰን ተደረገ

ማክሰኞ ህዳር 24 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለሲሚንቶ ፋብሪካ ድርጅቶች በጻፈው ደብዳቤ ከጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ  ምርታቸውን በፍትሃዊ ዋጋ  እንዲያቀርቡ መወሰኑን አስታውቋል፡፡

ከዚህ ቀደም የሲሚንቶ ምርት የፋብሪካ መሸጫ ዋጋ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እየተወሰነ ለገበያ ሲሰራጭ የቆየ ቢሆንም በአዲሱ የአሰራር ሂደት ግን አምራች ፋብሪካዎች ሙሉ ሀላፊነቱን በመውሰድ በነጻነት ምርታቸውን ለገበያ እንዲያቀርቡ እና ገበያውን እንዲያረጋጉ ሃላፊነት መስጠቱን ሚኒስቴሩ እውቁልኝ ብሏል፡፡

የሲሚንቶ ፋብሪካዎቹ የተሰጣቸውን ሀላፊነት በተጠያቂነት ስሜት እና በፍትሃዊ የዋጋ ተመን ማህበረሰቡን እንዲያገለግሉም መወሰኑን ገልጾ ከዚህ ቀደም አገልግሎት ላይ ይውል የነበረውን መመሪያ 940/2015 ማንሳቱን ይፋ አድርጓል ፡፡

ስለ ስራ!

03 Dec, 05:08


የስለ ስራ! ግሩፕ አድሚኖችን ያውቋቸዋል?
ተወዳጇቸው!

Zubeyda Awol ( @Zubenet
Ezedin Sultan ( @ezedin92
ሉላ ኢሳ ( @Yeamalenat
Mubarek Sadiq ( @Ibnusadik
Ina Omer ( @Inuyaa
Bin Ali ( @wdiali
ስለ ስራ ( @Selesera_bot

ፖስቶቻችሁን ፈትሾ አፕሩቭ ማድረግ፣ የተለያዩ ጠቃሚ መረጃዎች አዘጋጅቶ መፖሰት፣ ውይይት አቅራቢና ርዕስ በመምረጥ ውይይቶችን ማሰናዳት ከብዙ በጥቂቱ በአድሚኖች አማካኝነት የሚሰሩ ስራዎች ናቸው።

ግሩፑን የተመለከቱ ሀሳብና አስተያየታችሁን በተመቻችሁ ጊዜ ለቀረባችሁ የአድሚን አባላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

@ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

03 Dec, 04:18


የስለ ስራ! ግሩፕ አድሚኖችን ያውቋቸዋል?
ተወዳጇቸው!

Zubeyda Awel
Ezedin Sultan
ሉላ ኢሳ
Mubarek Sadik
Ina Omer
Bin Ali
ስለ ስራ

ፖስቶቻችሁን ፈትሾ አፕሩቭ ማድረግ፣ የተለያዩ ጠቃሚ መረጃዎች አዘጋጅቶ መፖሰት፣ ውይይት አቅራቢና ርዕስ በመምረጥ ውይይቶችን ማሰናዳት ከብዙ በጥቂቱ በአድሚኖች አማካኝነት የሚሰሩ ስራዎች ናቸው።

ግሩፑን የተመለከቱ ሀሳብና አስተያየታችሁን በተመቻችሁ ጊዜ ለቀረባችሁ የአድሚን አባላት ማቅረብ ትችላላችሁ።

@ስለ ስራ! የሁላችን ከሁላችን!

ስለ ስራ!

02 Dec, 15:20


National Bank of Ethiopia Issues Second Financial Stability Report

Link: https://nbe.gov.et/fsr/

ብሄራዊ ባንክ ሁለተኛው Financial Stability Report

ስለ ስራ!

02 Dec, 14:10


National Bank of Ethiopia Issues Second Financial Stability Report

Link: https://nbe.gov.et/fsr/

ብሄራዊ ባንክ ሁለተኛው Financial Stability Report

ስለ ስራ!

02 Dec, 10:14


ስለ ስራ! ከተመሰረተ በፈረንጆቹ 2025 ታህሳስ ላይ ሁለት አመት ይሞላዋል።

በቀሩት 45 ቀናት ውስጥ ስለ ስራ! ምን አዲስ ነገር ይዞ ቢመጣ ብለው ያስባሉ?

ስለ ስራ!

01 Dec, 10:34


#ፍራንኮቫሉታ

የጉሙሩክ ኮሚሽን በፍራንኮ ቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸው ሽቀጦች ከአንድ ወር ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ወደ ሃገር እንዲገቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

በፍራንኮ ቫሉታ ከውጭ የሚገቡ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በመደበኛ የንግድ ባንኮች የመተማመኛ ሰነድ /LC/ አማካኝነት እንዲገቡ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስትር ማስታወቁ ይታወሳል።

የጉምሩክ ኮሚሽን ህዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም. በፃፈዉ ደብዳቤ በፍራንኮ ቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸው ሸቀጦች በአንድ ወራት ባነሰ ጊዜ ዉስጥ ብቻ ወደ ሃገር ዉስጥ መግባት እንዳለባቸው አሳስቧል።

ኮሚሽኑ ይህን ያስተላለፈው የገንዘብ ሚኒስቴርን ዉሳኔ ተከትሎ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን ለሁሉም ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቶች እንዲያዉቁት አድርጓል።

መንግስት በመሰረታዊ የንግድ ሸቀጦች ላይ የምርት እጥረት እንዳይከሰት በማሰብ ለግል ባለሀብቶች ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ ይታወሳል፡፡

የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ.ም. በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት ፍራንኮ ቫሉታ መሰረታዊ ሸቀጦችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የምርት እጥረት እንዳይከሰት የተወሰነ እገዛ አድርጓል፡፡

ይሁን እንጂ የፍራንኮ ቫሉታ ባልተገባ መንገድ ለጥቁር ገበያ በመጋለጡ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ሲሉም ሚኒስትሩ ተናግረዋል ።

መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መደረጉንም የገለፁት አቶ አህመድ ሽዴ " በሂደት ላይ ያሉ ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንዲገቡ እንደሚደረግም " ተናግረው ነበር።

የጉምሩክ ኮሚሽን ከ ከጥቅም 28 ቀን 2017 ዓ.ም. በፊት የንግድ ሸቀጦች በፍራንኮቫሉታ ግዢ የተፈፀመባቸውን ሰነዶች በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ያስመዘገቡ እና በዋና መስሪያቤት በኩል የተረጋገጡ አስመጪዎች በአንድ ወር ዉስጥ የንግድ ሸቀጣቸዉን አጠቃለዉ ወደ አገር ዉስጥ እንዲያስገቡ ነዉ ማሳሰቢያ የሰጠዉ።

መረጃው የካፒታል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

19 Nov, 08:53


"የታክስ ደረሰኝ አጠቃቀም እና አስተዳደር መመሪያ /ማሻሻያ/ ቁጥር 188/2017" ምን አዲስ ነገር ይዟል?

አዲሱ መመሪያ ከህዳር 3 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ በፍትህ ሚኒስቴር ተመዝግቦ እና ጸድቆ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል።

- በመመሪያው መሰረት እያንዳንዱ የደረሰኝ ቅጠል ሲታተም ልዩ መለያ ኮድ (unique QR code) እንዲኖረው የሚያዝ ሲሆን ተካቶ ካልታተም ተቀባይነት አይኖረውም፡፡

- ማንኛውም አታሚ ደረሰኝ ሲያትም በታክስ ባለስልጣኑ የተዘጋጀውን ልዩ መለያ ኮድ (unique QR code) በመውሰድ በእያንዳንዱ የደረሰኝ ቅጠል ላይ አካቶ ሊያትም የሚገባው ሲሆን፤ ሲያትም የልዩ መለያ ኮዱ ወርድና ቁመት ቢያንስ 2 ሴንቲ ሜትር ሆኖ በደረሰኙ የቀኝ ራስጌ ላይ መታተም እንዳለበት ያዛል፡፡

- ማተሚያ ቤቱ ምንም አይነት ስህተት ወይም ልዩነት ሳይኖር ደረሰኞችን ልዩ መለያ ኮድ (unique QR code) በማካተት ለማተም በማንዋል ደረሰኝ QR- code (Manual Receipt QR-code Web Portal) የተጋራውን ዳታ በትክክል ተቀብሎ የመተግበር ግዴታ እንዳለበት አስቀምጧል።

- ማተሚያ ቤቱ በማንዋል ደረሰኝ QR-code አስተዳደር ፖርታል (Manual Receipt QR-code Web Portal) በኩል ዳታ ሲጋራ ተገቢነት ያላቸውን ሁሉንም የዳታ ጥበቃ ደንቦችና መመሪያዎችን የማክበር ግዴታ አለበት ይላል፡፡

- ማንኛውም ማተሚያ ቤት ልዩ መለያ ኮድ ያለው ማንዋል ደረሰኝ ሲያትም በወረቀቱ ላይ ሊሰርግ የሚችል ኢንክ ጀት (Ink jet) የሚባል ቀለም የመጠቀም ግዴታ አለበት፡፡

- ማንኛውም ማተሚያ ቤት እንዲታተም የተፈቀደውን እና የታተመውን ደረሰኝ በተመለከተ በተዘጋጀው ሲስተም በወቅቱ ሪፖርት የመላክ ኃላፊነት እንዳለበት አስቀምጧል፡፡

- ማንኛውም ማተሚያ ቤት በታክስ ከፋዩ ደረሰኝ እንዲያትም ሲጠየቅ፤ በታክስ ባለስልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የተሰጠ የደረሰኝ ህትመት ፈቃድ ደብዳቤ ሳይቀበል ደረሰኝ ማተም የለበትም፡፡

- በዚህ መመሪያ መሰረት የደረሰኝ ህትመት አገልግሎት የሚሰጥ ማተሚያ ቤት ከሚኒስቴሩ ጋር የቅንጅት አሰራር ስምምነት የማድረግ ኃላፊነት አለበት፡፡

በአዲሱ መመሪያ የመሸጋገሪያ ድንጋጌ መሰረትም:-

ማንኛውም ታክስ ከፋይ ይህ የማሻሻያ መመሪያ ተፈጻሚ ከመሆኑ በፊት አሳትሞ ያልተጠቀመባቸው ደረሰኞች መጠቀም የሚችለው የማሻሻያ መመሪያው ተፈጻሚ ከሆነበት ቀን ጀምሮ ባለው ለሶስት ወር ጊዜ ብቻ እንደሆነ አስቀምጧል፡፡

@tikvahethmagazine

ስለ ስራ!

18 Nov, 08:36


ከሳምንት በኋላ ዛሬም የመርካቶ ሱቆች በአብዛኛው ዝግ ሆነዋል

(መሠረት ሚድያ)- በዛሬው እለት በርካታ የመርካቶ ነጋዴዎች ሱቆቻቸውን ዝግ እንዳደረጉ ታውቋል፣ ምክንያቱ ደግሞ ከሰሞኑ በመንግስት አካላት እና በነጋዴዎች መካከል ውዝግብ የፈጠረው የገቢዎች የደረሰኝ አጠቃቀም ጉዳይ መሆኑ ታውቋል።

ነጋዴዎች እየተጠየቁ ያሉት የደረሰኝ ቅጣት እና የቅጣት አፈፃፀም ከአቅማቸው በላይ መሆኑን ሲናገሩ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ በበኩሉ በደረሰኝ እንዲገበያዩ የሚጠበቅባቸው ነጋዴዎች በደረሰኝ ግብይት እንዲፈጽሙ በመደረጉ ያነሱት ጉዳይ ነው ብሏል።

"በግምት ከዘጠና ፐርሰንት በላይ ሱቆች ዛሬ ዝግ ናቸው" ያለው አንድ ነጋዴ የመንግስት ባለስልጣናት ጭምር የተሳተፉባቸው የኮንትሮባንድ ምርቶች ወደ ገበያ ያለደረሰኝ እየተበተኑ ነጋዴውን ደረሰኝ ቁረጥ ማለት አግባብ አይደለም ብሏል።

ሌላ አንድ ስሜ አይጠቀስ ያለ የመርካቶ ነጋዴ የሱቅ መዝጋት አድማው "እስከ ስድት ቀን ሊቆይ ይችላል፣ እየተነጋገርን ነው" በማለት ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

መንግስት ያለደረሰኝ ግብይት ሲፈፅም የተገኘ ነጋዴ ንብረቶቹ ይወረሳሉ በሚል 'ሀሰተኛ መረጃ' አንዳንድ ባለንብረቶችና ነጋዴዎች ሱቃቸውን የመዝጋትና እቃዎችን የማሽሽ ሁኔታዎች አሉ ቢልም ነጋዴዎቹ የዛሬ ሳምንት ገደማ ይርጋ ሀይሌ የገበያ ማዕከል ደረሰኝ አልተቆረጠም በሚል ምክንያት ከ200 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችን ደንብ አስከባሪዎች እንሰወሰዱባቸው ተናግረዋል።

መረጃን ከመሠረት!

@MeseretMedia

ስለ ስራ!

13 Nov, 16:49


#ለመረጃ

ላኪዎች ከነገ ህዳር 5/2017 ዓም ጀምሮ ካመነጩት የውጭ ምንዛሪ 50 በመቶውን በመሸጥ ቀሪውን ላልተወሰነ ጊዜ በአካውንታቸው ማስቀመጥ ይችላሉ - ብሔራዊ ባንክ

ኅዳር 4/2017 (አዲስ ዋልታ) ላኪዎች ያመነጩትን የውጭ ምንዛሪ 50 በመቶ ወዲያውኑ በመሸጥ ቀሪውን 50 በመቶ ላልተወሰነ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ባለ አካውንታቸው ማስቀመጥ የሚችሉበት አሠራር ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምኅረቱ እንዳሉት ላኪዎች ካመነጩት የውጭ ምንዛሪ 50 በመቶውን ለባንኮች ወዲያውኑ በመሸጥ ቀሪውንም በአንድ ወር ውስጥ መሸጥ ይገደዱ ነበር።

በወቅቱ አሠራሩ በጊዜያዊነት ተግባራዊ ሲደረግ የተረጋጋ የውጭ ምንዛሪ ፍሰት እንዲኖር ከመፈለግ እንደነበርም አስታወሰዋል።

ከነገ ጀምሮ ግን ላኪዎች ያመነጩትን የውጭ ምንዛሪ 50 በመቶ ወዲያውኑ በመሸጥ ቀሪውን 50 በመቶ ላልተወሰነ ጊዜ በአካውንታቸው ማስቀመጥ ይችላሉ ብለዋል፡፡

ይህም ማለት ያመነጩትን የውጭ ምንዛሪ በአንድ ወር ውስጥ እንዲሸጡ አይገደዱም ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ስለ ስራ!

13 Nov, 12:39


ፍራንኮ ቫሉታ ለጥቁር ገበያ በመጋለጡ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር  ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ተባለ

ዕረቡ ህዳር 04 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በፍራንኮ ቫሉታ ከውጭ የሚገቡ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በመደበኛ የንግድ ባንኮች የመተማመኛ ሰነድ አማካኝነት እንዲገቡ መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ፍራንኮ ቫሉታ መሰረታዊ ሸቀጦችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የምርት እጥረት እንዳይከሰት የተወሰነ እገዛ ማድረጉን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ መግለጻቸው ተመላክቷል፡፡

ነገር ግን ፍራንኮ ቫሉታ ባልተገባ መንገድ ለጥቁር ገበያ በመጋለጡ በውጭ ምንዛሬ ላይ ጫና በማሳደር  ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ አመዝኗል ሲሉ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ  ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራው በመደበኛውና በትይዩ ገበያው መካከል ያለውን የውጭ ምንዛሬ ተመን ተቀራራቢ በማድረጉ የፍራንኮ ቫሉታ እንዲነሳ መደረጉን ገልጸዋል፡፡

አክለውም መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ውስጥ የማስገባት ውሳኔ ሙሉ በሙሉ እንዲቆም መደረጉን እና በሂደት ላይ ያሉ ከውጭ የሚገቡ ሸቀጦች በሁለት ሳምንታት ውስጥ እንዲገቡ እንደሚደረግም አመላክተዋል፡፡

በተጨማሪም የንግድ ባንኮች ለመረሰታዊ ሸቀጦች የሚሆን በቂ የውጭ ምንዛሪ ክምችት እንዳላቸው ጠቅሰው በውሳኔው መሰረትም ከውጭ የሚመጡ መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች በንግድ ባንኮች የመተማመኛ ሰነድ ብቻ እንዲገቡ መወሰኑንና ይህም ወደ ተግባር መግባቱን አረጋግጠዋል፡፡

መንግስት በመሰረታዊ የንግድ ሸቀጦች ላይ የምርት እጥረት እንዳይከሰት በማሰብ ለግል ባለሀብቶች ፍራንኮ ቫሉታ መፍቀዱ የሚታወስ ነው፡፡

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ

ስለ ስራ!

11 Nov, 12:05


የንግድ ፖሊሲዎች ተደጋግመው መውጣታቸው እና መቀያየራቸው ለስራ አስጊ እየሆነብን ነው ሲሉ ነጋዴዎች ቅሬታቸውን አሰሙ

ሰኞ ህዳር 02 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) በኢትዮጵያ የንግድ ፖሊሲዎች ተደጋግሞ መውጣት የንግድ ዘርፉን ስጋት ውስጥ እየጣለው ነው ሲሉ በአስመጪና ላኪ የስራ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡

በቅርቡ ክልከላ የተጣለበት የፍራንኮ ቫሉታ መመሪያ እንኳን ብዙ ነጋዴዎችን እና ባለሀብቶችን ችግር ውስጥ እያስገባ ስለመሆኑ የዘርፉ ባለሙያዎች ደጋግመው ሲገልጹ ይደመጣል፡፡

እንደነዚህ ያሉት ማሻሻያዎች ኢኮኖሚውን ለማረጋጋት ዓላማ ቢኖራቸውም ፣ ድንገተኛ ትግበራቸው እና በአጭር ጊዜ ውስጥ መቀልበሳቸው ብዙውን ጊዜ የንግድ ሥራዎችን በአግባቡ እንዳይካሄዱ እየዳረገ ነው ሲሉም ነው ቅሬታቸውን ለአዲስ ማለዳ ያሰሙት ።

ስማቸውን መጥቀስ ያልፈለጉ አንድ በቡና ንግድ ላይ የተሰማሩ ነጋዴ  እንዳሉት  በተደጋጋሚ የፖሊሲ ለውጦችን በኢኮኖሚው ላይ መተግበራቸው ለንግድ ድርጅቶች ቀጣይ እርምጃ ከፍተኛ ጥርጣሬን እየፈጠረ ነው ብለዋል።

“ኢኮኖሚው ከመንግስት የፖሊሲ መረጋጋትን ይፈልጋል ምክንያቱም ብዙ የኢንቨስትመንት ውሳኔዎች መወሰን ሚቻለው ያኔ ነው” ያሉት ቅሬታ አቅራቢው ፖሊሲዎች ከመተግበራቸው በፊት በደንብ ሊጠኑ እንደሚገባ አስምረው መንግስትም ከሚመለከታቸው የዘርፉ አካላት ጋር እንዲወያይ ጠይቀዋል፡

የምጣኔ ሃብት ባለሙያው አጥላው ዓለሙ (ዶ/ር) በበኩላቸው የሚቀያየሩት ፖሊሲዎች የንግድ ባለቤቶች ረጅም ለማቀድ እንዳይችሉና ጥርጣሬ እንዲፈጥርባቸው እንደሚያደርጋቸው ጠቁመዋል፡፡

አክለውም ድርጅቶች በፖሊሲዎች ላይ ሊደረጉ የሚችሉ ለውጦችን በመገመት አሳሳቢ ጉዳዮቻቸውን እና ስራዎቻቸውን በረጅም እቅድ  ላይ ከማተኮር ይልቅ በአጭር ጊዜ እቅድና የንግድ እንስቃሴ እንዲገደቡ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመጣው የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ የቢዝነስ ተቋማት ፈጣን የፖሊሲ ሽግሽግ የሚያስከትለውን መዘዝ ለመዳሰስ ፈታኝ እየሆነባቸው እንደሆነ ተደጋግሞ ይነሳል።

ምንጭ አዲስ ማለዳ

ስለ ስራ!

09 Nov, 05:28


#ሲሚንቶ

" ከዛሬ ጀምሮ በሚኒስትር መ/ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ቀርቷል " - ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ዶ/ር ካሳሁን ጎፌ ከሲሚንቶ አምራቾች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል።

በዚህም ወቅት " ከዚህ ቀደም በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በኩል ይደረግ የነበረዉ የሲሚንቶ ግብይት ትስስር ሥራ ከዛሬ ጀምሮ ቀርቷል " ብለዋል።

አምራቾች በራሳቸዉ ኃላፊነት በሚመርጧቸዉ አከፋፋዮችና ቸርቻሪዎች በኩል ለተጠቃሚዎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡

የሲሚንቶ ገበያዉን ለማረጋጋት ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል ይደረጋል ያሉ ሲሆን የአፈጻጸም ሪፖርት ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በማያቀርቡ በማናቸዉም የሲሚንቶ አምራች ላይ " የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ሚኒስትሩ " አዲሱን ዉሳኔና አቅጣጫ ተከትሎ በግብይት ሰንሰለቱ የደላላ ጣልቃ ገብነት የከሰመ፣ ለመንግስት ፕሮጀክቶችና ለተጠቃሚዉ ህብረተሰብ አስተማማኝ የሲሚንቶ አቅርቦት የተረጋገጠ፣ አምራቾችም ተገቢዉን ትርፍ እያገኙ የከምፓኒዎቻቸዉን ዘላቂ ዕድገት የሚያስቀጥሉበት እንዲሆን " ብለዋል።

የግብይት ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ ከካሽ ክፍያ ነጻ ሆኖ በዲጂታል ክፍያ ሥርዓት እንዲፈጸም አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

በውይይት መድረኩ ወቅት አምራቾች የምርት አቅማቸውን እንዲያሳድጉ ተብሏል።

ሲሚንቶ አምራቾች አዲሱን ውሳኔ በማክበር እንደሚተገብሩ ተናግረው ነገር ግን የማምረቻ ግብዓት ፣ የኃይል አቅርቦትና ተያያዥ ችግሮች እንዲፈቱላቸዉ ጠይቀዋል፡፡

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

08 Nov, 18:08


ብሔራዊ ባንክ የፃፈው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል

ስለ ስራ!

08 Nov, 17:59


ሞኤንኮ ፥ በኢትዮጵያ የቢዋይዲ (BYD) ኤሌክትሪክ እና ሃይብሪድ ተሸከርካሪዎች ይፋዊ አከፋፋይ መሆኑን ገለጸ።

በኢንችኬፕ ኩባንያ ስር የሚተዳደረው ሞኤንኮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መረጃ ፥ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ቴክኖሎጂ ዓለም አቀፍ መሪ ከሆነው ቢዋይዲ (BYD) ጋር በኢትዮጵያ የቢዋይዲ የኤሌክትሪክ እና ሃይብሪድ ተሸከርካሪዎች ዋና አከፋፋይ ለመሆን የሚያስችለውን ስምምነት መፈራረሙን ገልጿክ።

በስምምነቱ ሞኤንኮ በኢትዮጵያ በዋናነት የቢዋይዲ (BYD) ተሽከርካሪዎችን የሚያከፋፍል ይሆናል።

ሞኤንኮ ከታህሳስ 2017 ጀምሮ ለአካባቢ አየር ተሰማሚ እና በቴክኖሎጂ የተራቀቁ የቢዋይዲ ተሸከርካሪዎችን ከአስተማማኝ ጥገና ፣ መለዋወጫ እና ዋስትና ጋር እንደሚያቀርብም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

" ይህ ስምምነት ዘላቂና አዳዲስ ቴክኖሎጅዎችን የማስተዋወቅ እና ለማቅረብ ያለንን ቁርጠኝነት ያሳያል ' ብሏል።

የኢንችኬፕ አፍሪካ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ፍራንሲስ አግቦንላሆር ፥ " ይህ አጋርነት ለኢትዮጵያ የተሸከርካሪ ኢንዱስትሪ ወሳኝ አስተዋጽዖ ያበረክታል ፤ ይህም የአዳዲስ ፈጠራ መስፋፋት እና ታዳሽ ሀይልን በመጠቀም ዘላቂ የሆነ የትራንስፖርት አገልግሎትን ያፋጥናል " ብለዋል።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

08 Nov, 17:57


ገንዘብ ሚኒስቴር በፍራንኮ ቫሉታ የሚገቡ ምርቶች ላይ ክልከላ ጣለ

አርብ ጥቅምት 29 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) ዘይትን ጨምሮ ያለውጭ ምንዛሬ ፍቃድ በፍራንኮ ቫሉታ ይገቡ የነበሩ ምርቶች ላይ ሚኒስቴሩ ክልከላ እንዳደረገ ነው የገለጸው፡፡

በቅርቡ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሺያ ዘላቂ በሆነ መንገድ ውጤታማ እንዲሆን ከማስፈለጉ አንጻር ይህን ውሳኔ መወሰን የግድ ሆኖ መገኘቱም ነው የተገለጸው፡፡

በፍራንኮ ቫሉታ ግዢ የተፈጸመባቸው እቃዎችም ከዛሬ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ጀምሮ በ15 ቀናት ጊዜ ውስጥ አስፈላጊውን የጉምሩክ መስፈርት በማሟላት እቃቸውን ማውጣት እንደሚገባቸው የገለጸው ገንዘብ ሚኒስቴር ይህን እንዲያስፈጽሙም ለጉምሩክ ኮሚሽንና ለብሄራዊ ባንክ ደብዳቤን ልኳል፡፡

በገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ ተፈርሞ የወጣው ደብዳቤው በቀጣይ ዘይትን ጨምሮ በፍራንኮ ቫሉታ ይገቡ የነበሩ ምርቶች  በምን አግባብ በአዲስ አሰራር ይቃኛሉ የሚለው ላይ ግን ግልጽ የሆነ ማብራሪያን አላስቀመጠም፡፡

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ

ስለ ስራ!

07 Nov, 09:59


ብሔራዊ ባንክ ለሁሉም የክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች የዲጂታል ክፍያ በQR ኮድ እንዲሆን ትዕዛዝ መስጠቱን ገለጸ

ሐሙስ ጥቅምት 28 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ለሁሉም የክፍያ አገልግሎት ሰጪዎች የዲጂታል ክፍያ በQR ኮድ ከህዳር 22 ቀን 2017 ጀምሮ ተግባራዊ እንደያደርጉ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

አዲሱ መመሪያ ከጥሬ ገንዘብ ንክኪ ነጻ የሆነውን የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት በኢትዮጵያ ለማጎልበት እየተሰራ ያለውን ስራ ለማጠናከር እንደሚያግዝ እና የዲጂታል ግብይትን እየለመደ ያለውን ማህበረሰብ በይበልጥ የሚያጠናክር መሆኑ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም ይህ ኢት ኪውአር ኮድ (EthQR Code) የሚል ሥያሜ የሚኖረው አሠራር ዓለምአቀፍ የአሠራር ልምዶችን መሠረት ያደረገ፣ የክፍያም ሆነ የግብይት ተዋናያንን ሙሉ መረጃ የሚይዝ ነገር ግን ከተወሰኑ አስፈላጊ መረጃዎች በቀር ሌሎቹን በምሥጢር የሚጠብቅ  ሥርዓት መሆኑ ተገልጿል።

ባንኩ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የዲጂታል ክፍያ አገልግሎትና ግብይት የጥሬ ገንዘብን ዝውውር የሚቀንስ ከመሆኑም በላይ፣ ሕብረተሰቡ ለሥርቆት፣ በእጁ ያለው ገንዘቡም ለእርጅና እንዳይጋለጥ፤ ከባንክ ውጭ የሚዘዋወር የገንዘብ መጠን እንዲቀንስ፣ ብሎም በአገር አቀፍ ደረጃ ገንዘቡን ለማሳተም የሚወጣ ወጪን እንዳይጨምር ለማድረግ ይረዳል ብሏል።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ

ስለ ስራ!

30 Oct, 08:13


#ለመረጃ፡ የጉምሩክ ኮሚሽን በራሳቸው የውጭ ምንዛሪ (ፍራንኮ ቫሉታ) ጥሬ ዕቃ ወደ አገር ውስጥ የሚያስገቡ ኩባንያዎች የሚያቀርቧቸው የኤሌክትሮኒክ የማጓጓዣ ሰነዶች ተቀባይነት አግኝተው እንዲገለገሉ ፈቀደ፡፡

ሪፖርተር የተመለከተውና በጉምሩክ ኮሚሽነሩ አቶ ደበሌ ቃበታ ተፈርሞ ለሁሉም የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ለሚፈጸምባቸው ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች የተመራው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው፣ ሌሎች በሕግ የተገለጹ ደጋፊ ሰነዶች መሟላታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በራሳቸው የውጭ ምንዛሪ (ፍራንኮ ቫሉታ) ሥርዓት ጥሬ ዕቃ ወደ አገር የሚያስገቡ ኩባንያዎች ብቻ የሚያቀርቡት የቴሌክስ ሪሊዝ (Telex Release)፣ ሲ ዌይቢል (Sea Waybill) ሰነዶች እንደ መጓጓዣ ሰነድ ተቀባይነት አግኝተው ተገቢው አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡

ቴሌክስ ሪሊዝ (Telex Release) ግዥ ለተፈጸመበት ዕቃ መርከብ ላይ መጫኑ ሲረጋገጥ አጓጓዡ ወይም የአጓጓዡ ወኪል (Agent) በየትኛውም ቅርንጫፍ ዋናውን ቅጂ በማስገባት (Surrendered)፣ ሰነዶቹን የተቀበለው አጓጓዥ ድርጅትም ሆነ የአጓጓዡ ወኪል ዋናውን ቅጂ መቀበሉን በማረጋገጥ ለመዳረሻ ወደብ (Destination Port) ዕቃው እንዲለቀቅ በኤሌክትሮኒክ መልዕክት የሚያስተላልፍበት ሥርዓት ነው፡፡

ሲ ዌይቢል (Sea Waybill) ደግሞ አጓጓዡ ድርጅት (Carrier/Shipping Line) ዕቃውን ስለመቀበሉ የሚረጋገጥበትና የመጓጓዣ ውል ማስረጃ ሆኖ የሚያገለግል ሰነድ ሲሆን፣ መዳረሻ ወደብ ደርሶ ክሊራንስ ከመጠናቀቁ በፊት ባለቤትነት ማስተላለፍ የማይቻልበት ነው፡፡

በተለያዩ የኢንዱስትሪ ፓርኮችና ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ውጪ የሚገኙ አምራቾች ጥሬ ዕቃ ወደ አገር ውስጥ ሲያስገቡ ቴሌክስ ሪሊዝ (Telex Release) እንዲሁም ሲ ዌይቢል (Sea Waybill) የማጓጓዣ ሰነድ እንደሚጠቀሙ በመግለጽ፣ በእነዚህ ሰነዶች አገልግሎት እንዲሰጣቸው ለጉምሩክ ኮሚሽን ጥያቄ ሲያቀርቡ መቆየታቸው ታውቋል፡፡

የዕቃ ዲክላራሲዮን በኤሌክትሮኒክ ሰነድ መቅረብ እንደሚችልና ወደ አገር ለሚገቡና ለሚወጡ ዕቃዎች ላይ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት ለመፈጸም የሚቀርቡ ደጋፊ ሰነዶችን ለመወሰን ሥልጣን የተሰጠው ኮሚሽኑ፣ የተሻሻለውን የጉምሩክ አዋጅ 859/2014 መሠረት በማድረግ ኩባንያዎች ውጭ አገር ከሚገኝ ላኪ ድርጅት ጋር ባላቸው ስምምነት መሠረት የሚላኩላቸውን ጥሬ ዕቃዎች ለመቀበል የሚጠቀሙበት ሥርዓት በመሆኑ ውሳኔውን ተግባራዊ ማድረግ እንዳስፈለገ አስታውቋል፡፡

ጉምሩክ ኮሚሽን እንዳስታወቀው ቴሌክስ ሪሊዝና ሲ ዌይቢል ሥርዓት በሌሎች አገሮችም ንግድን ለማቀላጠፍ ተግባራዊ የሚደረግ ነው፡፡

ሪፖርተር ያነጋገራቸው የሎጂስቲክስ ባለሙያዎች በሰጡት አስተያየት የጉምሩክ ኮሚሽን ቴሌክስ ሪሊዝና ሲ ዌይቢል እንደ ሕጋዊ የማጓጓዣ ሰነድ አድርጎ መቀበሉ፣ ኢትዮጵያን ከዓለም አቀፍ ዕቃዎች የማጓጓዝ ስታንዳርድ ጋር የሚያስተሳስር ነው ብለዋል፡፡

ባለሙያዎቹ በተጨማሪም ኮሚሽኑ የፈቀደው ይህ ሥርዓት የሎጂስቲክስና የጭነት አስተላላፊነት አገልግሎት አሠራርን ከማስተካከል ባሻገር፣ ፍጥነትና ቅልጥፍናን እንደሚጨምር አስረድተዋል፡፡
መረጃው የሪፖርተር ነው!

ስለ ስራ!

21 Oct, 16:41


#ደመወዝ : የደመወዝ ጭማሪ ተፈቅዶና በጀቱም ጸድቆ ክፍያው ከጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም.  ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዛሬ አሳውቋል።

ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል።

(ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል)

#CivilServiceCommission
#MekuriaHaile

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

18 Oct, 10:42


ከዚህ በፊት የቅዳሜ ውይይታችን ላይ እንግዳ የነበሩት አቶ ኢብራሂም አብዱ የሚከተለውን ሀሳብ በገፃቸው አጋርተዋል
===============
የኢትዬ ቴሌኮም ሼር ልግዛ ወይንስ አልግዛ?

ሼር ለመግዛት ስናሰብ የድርጅቱን አሰተዳደራዊና የፋይናንስ ጤንነት ማረጋገጥ አለብን። የአንድ ድርጅት የፋይናንሰ ጤንነት ለማወቅ መጠናዊ (quantitative)እና አይነታዊ (qualitative) መለኪያዎች አሉ።

✍🏽 ቀዳሚው የድርጅት ፋይናንሰ መጠናዊ መለኪያ አጠቃላይ የገበያ ዋጋ (Market Capitakization) ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ለአክሲዮን ሸያጭ ያወጣው የሸያጭና የድርጅት ቁመና መግለጫ ሪፖርት (prospectus) እንደሚያሳየው የእያንዳንዱ ዋጋ 300 ብር የሆነ አጠቃላይ 1 ቢሊየን ሼሮች አሉት። ይህም ማለት አጠቃላይ የገበያ ዋጋዬ ነው ብሎ ያሰቀመጠው 300 ቢሊየን ብር ነው። ከዚህ ውሰጥ ለሽያጭ የቀረበው እያንዳንዳቸው 300 ብር የገጽ ዋጋ ያላቸው 1 ሚሊየን ሼሮችን ነው። የድርጅቱ አጠቃላይ የገበያ ዋጋ 300 ቢሊየን ነው ስለተባለ ነው ማለት አይደለም። ይሄ የሚያመለክተን የሼሮቹን ዋጋ ወይም በስቶክ ማርኬት ውስጥ የሚኖረውን ዋጋ ነው። የሚጠቅመንም ኢንደስትሪው ውስጥ ካሉ ሌሎች ተመሳሳይ ድርጅቶች ጋር ለማነጻጸር ነው። የድርጅቱን ትክክለኛ ዋጋ የምናውቀው Enterprise value በማሰላት ነው። ይህ በቀላሉ የድርጅቱን የገበያ ዋጋ ላይ ድርጅቱ ያለበትን ብድር በመደመርና ያለውን ጥሬ ገንዘብ በመቀነስ ማስላት ይቻላል። በተጨማሪ አይነታዊ የሆኑ መለኪያዎችን በመጨመር ድርጅቱ ያለውን ሀብት፥ የዘረጋውን መሰረተ ልማት፥ የሰበሰባቸውን ደንበኞች፥ ማፍለቅ የሚችለውን ገቢ፥ የገነባውን ብራንድ፥ በገበያው ውስጥ ያለውን ድርሻ እንዲሁም ያለበትን እዳ ግምት ውስጥ አሰገብተን ማሰላት እንችላለን።

✍🏽 የገቢና የትርፍ (Revenue& Earning)ልኬት ነው። ቢያንሰ ባለፉት አምስት አመታት የድርጅቱ ገቢ ምን ያክል ነበር? በምን ያህል እያደገ ነው? የትርፉ ምጣኔስ? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ማስላትና ሂደቱን መረዳት እንችላለን። ለምሳሌ የኢትዬ ቴሌኮምን የገቢና ትርፍ እድገት ስንመለከት በ 2020 ገቢው 56 ቢሊየን ብር አካባቢ የነበረ ሲሆን በሰኔ 2024 ደግሞ 93•7 ቢሊየን ብር ደርሷል። ይህ በአማካይ የገቢው እድገት 21% አካባቢ እንደሆነ ያሳያል።

✍🏽ሌላው የፋይናንሰ ጤንነት መለኪያ የሼር ገቢ (Earning per share)ነው። በዚ ቀመር የድርጅቱ አንድ ሼር በአመቱ ምን ያክል የትርፍ ምጣኔ አገኘ የሚለው ይሰላል።
ለምሳሌ: ኢትዬ ቴሌ ኮም ባለፈው የሂሳብ አመት የተጣራ ትርፉ  21•79 ቢሊየን ብር እንደሆነ ተገልጽዋል። ይህ ትርፍ ድርጅቱ ላለው አጠቃላይ የሼር ብዛት (1 ቢሊየን) ሲካፈል 21•79 ብር የሼር ገቢ ምጣኔ ይኖረዋል። ይህም ማለት አንድ ሼር 21•79 ብር ትርፍ ይኖረዋል። አሁን ባለው የሼር ዋጋ አንዱ ሼር 300 ብር የሚሸጥ በመሆኑ የ 300 ብር ኢንቨሰትመንት በአመት 22 ብር አካባቢ ትርፍ ያሰገኛል። ይህ ትርፍ ያለፉት አመታት እድገቱን ከተከተለ በየአመቱ በአማካይ 21 ፐርሰንት እያደገ ይሄዳል።

✍🏽ሌላኛውና ወሳኝ የሚባለው የፋይናንሰ መለኪያ PEG ratio ይባላል። የአንድ ሼርን ትርፍ እድገትን ግምት ውስጥ አሰገብተን የምናሰላበትና የሼሩ ዋጋ ተገቢ ነው? በዝቶበታል? ወይንስ ርካሸ ነው የሚል የሚያመላክተን ነው።

የቴሌን ምሳሌ ቀጠለን ብንመለከተው የአንድ ሼር ትርፍ 22 ብር አካባቢ እንደሆነ አይተናል። ይህን የአንድ ሼር ትርፍ ለአመታዊ እድገቱ ማለትም 21 ፐርሰንት (በሙሉ ቁጥር) ሰናካፍለው 1•04 አካባቢ ይመጣል። የአንድ ሼር PEG ratio ከ1 በላይ ከሆነ የሼር መሸጫ ዋጋው ውድ መሆኑን ያመላክታል።

✍🏽ከነዚህ በተጨማሪ ለውሳኔ የሚያግዙን ንፅፅራዊ የሆኑ የፋይናንሰ ጤንነት መለኪያዎች አሉ። ከነዚህ ቀዳሚው የሼር ትርፍ ንጻሬን(EPS ratio) ከሌሎች ትርፎች ጋር ማነጻጸር ነው። ከላይ እንዳየነው የኢትዬ ቴሌኮም የአንድ ሼር ትርፍ 22 ብር አካባቢ ነበር። ይህን ትርፍ በአንድ ሼር መሽጫ ዋጋ ስናካፍለው (22/300)= 7 ፐርሰንት አካባቢ ነው። ሰለዚህም ባለፈው የሂሳብ አመት የቴሌ ሼር የትርፍ ምጣኔ 7 % ብቻ ነበር። ይህ ደግሞ ከባንክ የቁጠባ ወለድ በታች ከመሆኑ በተጨማሪም ከሌሎች ኢንቨሰትመንቶች የትርፍ ምጣኔ ያነስ ነው።

✍🏽 ግምት ውስጥ መግባት ካለበት የአይነታዊ መለኪያ አንዱ የድርጅቱ የቢዝነሰ ሞዴል የእድገት ተስፋ ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ከቴሌኮም ሰርቪስ በተጨማሪ ግዙፉ የዲጂታል ፋይናንሰ(Fin-Tech) ተቋም እየሆነ መጥቷል። ይህም የድርጅቱን እድገት ብሩህ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዬ ቴሌኮም ለመሰረተ ልማት ዝርጋታ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ያፈሰሰ በመሆኑ ባለፉት አመታት ትርፉ ያነስ የመሆን እድሉና ወደፊት የማደግ ተሰፋ እንዳለው አመላካች ነው።

✍️የአንድ ድርጅትን ሼር ለመግዛት እነዚህ መለኪያዎች በቂ አይደሉም። ወሳኙ መለኪያ መግዛት የፈለግንበት ምክኒያት ነው።  ከትርፍ ባሻገር ባለቤት የመሆን፥ ተጽዕኖ የመፍጠር፥ ውርስ የመሳሰሉ ምክኒያቶች ሊኖሩን ይችላሉ። ሌላው እጃችን ላይ ያለው የገንዘብ መጠንና ያሉን አማራጭ ኢንቨሰትመንቶች ውሳኔያችን ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል።

ስለ ስራ!

18 Oct, 06:08


"የኢትዮ ቴሌኮምን ሼር እንግዛ ወይ?"

ታዋቂው የንግድ አማካሪ እና አሰልጣኝ ጌቱ ከበደ በማህበራዊ ሚድያ አድራሻቸው የሚከተለውን አስፍረዋል።
=========================

"የኢትዮ ቴሌኮምን ሼር እንግዛ ወይ?"

ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነው። የዚህ ዓይነት ጥያቄ ከሀገር ውስጥም ከውጭ ሀገርም በውስጥ በኩል እየቀረበልኝ ነው። በተመሳሳይ ለአንዳንድ ወዳጆቼም እንዲህ ዓይነት ጥያቄ እንደቀረበላቸው እገምታለሁ።

ለእንደዚህ ዓይነት ጥያቄ "ግዙ" ማለትም "አትግዙ" ማለትም ተገቢ አይሆንም። ምክንያቱም ብዙ የማይታወቁ መረጃዎች ስላሉ ነው።

ለእያንዳንዱ ግለሰብ ውሳኔ እንዲረዳ ግን አንዳንድ ነጥቦችን ማየት ይጠቅማል።

፩) አብዛኛው አክሲዮን የተያዘው በማን ነው?

ከ20-25 % በላይ የሚሆነው አክሲዮን በ1 አካል ከተያዘ ትኩረትን የሚስብ ነው። በ1 አካል የተያዘው አክሲዮን ከ33% በላይ ከሆነ ደግሞ አሳሳቢ ነው። 50% በላይ ከሆነ ደግሞ ያንን አክሲዮን መግዛት አደገኛ ነው። ከ75% በላይ አክሲዮን በ1 አካል ከተያዘ ደግሞ የተለየ ምክንያት ከሌለህ እና አክሲዮን ሻጩን በጣም የምታምነው ካልሆነ በቀር አክሲዮን የምትገዛበት ልዩ ምክንያት ያስፈልግሃል።

ምክንያቱም ባለ ብዙ አክሲዮኑ በፈለገ ጊዜ አክሲዮን እያወጣ እየሸጠ ያንተን ድርሻ ያመነምነዋል። ይህ Dilution (ማቅጠን) ይባላል። ለምሳሌ : 1% ቢኖርህ ባለ ትልቅ አክሲዮኑ አዲስ አክሲዮን በመሸጥ ድርሻህን ወደ 5% ሲለው ደግሞ ወደ 0.5% ያወርደዋል። አንተም እያየኸው ሼርህ ይሟሟል። ብር ምንዛሪው ሲቀንስ አላየህም? እያየኸው ዓቅሙ አልላሸቀም? እንደዚያ ማለት ነው።

ECX ላይ መጀመሪያ ወንበር ሲሸጥ ለ100 ገዢዎች ብቻ ተብሎ ነበር የተሰበከው። በኋላ ግን ያለገዢዎች ምክክር ወደ 400 አደገ። አሁን ስንት እንደሆኑ አኣውቅም። በንግድ ስትሻረክ መተማመን ወሳኝ ጉዳይ ነው።

አንድ 3/4ኛ ድርሻ ያለው አካል ካለ፣ ውሳኔው በሙሉ በእርሱ ቁጥጥር ስር ነው። ያ ችግር የማይኖረው፣ ውሳኔ ሰጪው አንድም ታማኝ ሲሆን፣ ሲቀጥልም አንተ ሌላ አማራጭ ሳይኖርህ ቀርቶ ይህ እድል በልዩነት ሲሰጥህና አንተም ተስፋ ስታደርግበት ነው።

የኢትዮቴሌኮም ኢንዱስትሪ አሁን ባለው ሁኔታ አትራፊ ነው። አትራፊ መሆኑ ብቻ ግን አዋጭ ኢንቨስትመንት ነው ማለት አይደለም። ሌሎች መታየት ያለባቸው ጉዳዮች ይኖራሉ።

አሁን በተነገረው መሠረት መንግስት 90% ድርሻን ይዞ 90% ለሌሎች የሚሸጥ ነው። የመንግስት ድርሻ ከ30% ባይበልጥ ግሩም ነበር።

የባለቤቱ (የመንግስት) ታማኝነት ዋናው ጉዳይ ነው። አሁን ባለው የ90% አክሲዮን ድርሻ ሁኔታ መንግስት ሌሎች ባለአክሲዮኖችን ሳያወያይ ዋና ዋና ጉዳዮችን መቀየር የሚያስችል መብት ህጉ ይሰጠዋል። አንተ ባለ ትንሽ አክሲዮኑ የተባለውን ከመቀበል ውጪ መብት የለህም።

የምታምነውና በጥሩ % ትርፋማ የሆነ እና በየዓመቱ ትርፍ የሚያከፋፍል አክሲዮን ሻጭ ካገኘህ ግን 0.001% ድርሻም ትልቅ ነውና ብትገዛ ጥሩ ነው።

ባለ ትልቅ አክሲዮኑ ፈቃደኛ ካልሆነ ግን ድርጅቱ አትርፎም ትርፍ እንዳይከፋፈል ሊወስን ይችላል። አንተም ሁሌ ወሬህ አክሲዮን አለኝ ከማለት ባለፈ "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም እላይ" እያልህ መክረም ነው። እንደዚያ የሆኑ ብዙ የሀገራችን አክሲዮኖች አሉ።

መንግስት "ቴሌ የምትታለብ ላም ናት" ሲል ከርሞ አሁን ለምን አክሲዮኑን ይሸጣል? የዚህ ምክንያት እንደየአመለካከታችን ይለያያል። ዋናው ምክንያት የሚመስለኝ የገንዘብ ግሽበትን ለመቆጣጠር ገበያ ውስጥ ያለውን ብር መምጠጥ ነው። ይሄ በታክስ፣ ቅጣት እና የመንግስት አገልግሎቶች ዋጋ መናር የታየ ነው።

መንግስት እያደረገ ያለው ነገር ሲታይ ለዜጎች ትርፍ ማጋራት አስቦ አይመስልም። ይልቅስ ተቀማጭ ገንዘብ ካላቸው ግለሰቦች ላይ ገንዘባቸውን መምጠጥ ይመስላል። አይደለም ያላችሁም ልክ ትሆኑ ይሆናል። ለእኔ የታየኝ ግን እንዲያ ነው።

፪)

፫)

፬)

ብዬ የማቀርባቸው ሌሎችም ማብራሪያዎች ነበሩኝ። ግን ምን አስጨነቀኝ? ለገባው ይሄው 1 ምክንያት በቂ ነው።

ውሳኔውን ግን በራሳችሁ ወስኑ።

ስለ ስራ!

15 Oct, 12:04


አዲሱን የብሔራዊ ባንክ መመሪያ ተከትሎ ባንኮች በውጭ ምንዛሬ ላይ እስከ አስራ አንድ ብር የሚደርስ ቅናሽ ማሳየታቸው ተገለጸ

ማክሰኞ ጥቅምት 05 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) ብሄራዊ ባንክ አዲስ ባወጣው መመሪያ ባንኮች በየቀኑ በሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ የመሸጫና የመግዣ መጠን ላይ ልዩነቱ ከሁለት በመቶ በላይ እንዳይሆን ማስታወቁን ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የዶላር መሸጫ ዋጋቸው ላይ ቅናሽ አሳይተዋል፡፡

በዚህ የግብይት ሂደት ውስጥ ያሉ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ የመሸጫ እና የመግዣ ዋጋቸውን በየዕለቱ እየወሰኑ ይፋ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን፣ በአብዛኛዎቹ ባንኮች በዶላር መግዣ እና መሸጫ ዋጋቸው መካከል ያለው ልዩነት ከ10 በመቶ በላይ መድረሱ ተጠቁሟል።

በመሆኑም ብሔራዊ ባንክ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ባስተዋወቀው አዲስ ፖሊሲ ባንኮች በውጭ ምንዛሪ የመግዣ እና የመሸጫ ዋጋ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ መብለጥ እንደሌለበት ወስኗል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ባወጣው ዕለታዊ የውጭ ምንዛሬ ግብይት የዋጋ ዝርዝር ላይ የዶላር የመሸጫ ዋጋው ከትናንቱ ጋር ሲነጻጸር የስምንት ብር ቅናሽ ያሳየ ሲሆን የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ደግሞ የአስራ አንድ ብር ቅናሽ አድርጓል፡፡

ብሔራዊ ባንክ አዲሱን መመሪያ በተመለከተ ለሁሉም ባንኮች በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን እስከ ረቡዕ ድረስ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አዟል።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ

ስለ ስራ!

15 Oct, 11:55


ባንኮች የውጭ ምንዛሬን የሚገዙበትና የሚሸጡበት የልዩነት መጠን ከ2 በመቶ እንዳይበልጥ የሚገድብ መመሪያ ይፋ ሆነ፡፡

ማክሰኞ ጥቅምት 05 ቀን 2016(አዲስ ማለዳ)ብሄራዊ ባንክ አዲስ ያወጣው መመሪያ ባንኮች በየቀኑ በሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ የመሸጫና የመግዣ መጠን ላይ ልዩነቱ ከሁለት በመቶ በላይ እንዳይሆን የሚገድብ እንደሆነም አስታውቋል፡፡

ለሙሉ ዘገባ፡ https://addismaleda.com/archives/39311

ስለ ስራ!

15 Oct, 08:42


የስለስራ! እንግዳችን የነበሩት አቶ ሙከሚል በድሩ በቅርቡ ንግድ ባንክ ያዘጋጀሁትን የውጭ ምንዛሬ ነጋዴዎች አልተጠቀሙትም ማለቱን ተከትሎ ለምን ይህ እንደተፈጠረ ያብራሩበትን ምስል አጋርተናችኋል!

ስለ ስራ!

12 Oct, 17:09


የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት
ግብይትና ግመታ ረቂቅ አዋጅ አጭር ማብራሪያ

ስለ ስራ!

11 Oct, 03:25


#ሪልስቴት

ያልተገነባ ቤት / ግንባታ ከማከናወናቸው በፊት ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ አካውንት እንዲያስቀምጡ ሊገደዱ ነው ፤ በተጨማሪ ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ሊከለከሉ ነው።

ይህንም የሚመለከት ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ቀርቧል።

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?

ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን #እንዳይመዘግቡ እና #ቅድመ_ክፍያ እንዳይሰበስቡ ይከለክላል።

በአሁኑ ጊዜ ባለው አሠራር መሠረት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ብቻ ወደ ሪል ስቴት ገበያው ሲቀላቀሉ የነበሩት አልሚዎች፤ በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ " የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ " የማውጣት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሀብት ሪል ስቴት አልሚዎች ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ቢያንስ 50 ቤቶችን ገንብተው የሚያስከረክቡ መሆን አለባቸው።

የአገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች ግንባታውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን " የፋይናንስ አቅርቦት ምንጭ " የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦባቸዋል። ይሁንና ረቂቁ፤ " የቅድሚያ ቤት ሽያጭ ተጠቃሚነት " መብትን ከቅድመ ሁኔታ ጋር ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሰጥቷል።

ይህ አሠራር የሪል ስቴት አልሚዎች የቤት ግንባታውን ሳያከናውኑ ወይም በሂደት ላይ እያለ ለግንባታው የሚውልን ፋይናንስ የሚያሰባስቡበት እና ገንዘቡብ ለግንባታው የሚያውሉበት መንገድ ነው።

የቤት ግንባታው ሳይከናወን በፊት ከገዢዎች ጋር ውል ማሰር እና ክፍያ መፈጸም ኢትዮጵያ ውስጥ በሪል ስቴት ልማት ላይ በተሰማሩ አልሚዎች በኩል የተለመደ አሰራር ነው።

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ለግንባታ የሚውለውን ሀብት ማሰባሰብ የሚፈልጉ አልሚዎች " አግባብ ካለዉ አካል ፈቃድ ማቅረብ " ይጠበቅባቸዋል። ይህም ግዴታ ነው።

የቅድመ ሽያጭ ዘዴን መጠቀም የሚፈልጉት ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡት ገንዘብ የሚቀመጥበት የባንክ ሂሳብ እና የገንዘብ አወጣጥ ላይም አስገዳጅ አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተጥሎባቸዋል።

አልሚዎቹ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ " የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ " እንዳለባቸው ረቂቅ ሕጉ ላይ ሰፍሯል።

አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው " አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት " እንደሆነም ያስረዳል።

በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ ይወሠናል።

ከዚህም ባሻገር በቅድሚያ የተሸጠው ቤት ተገንብቶ ለተጠቃሚዎች እስከሚተላለፍ ድረስ የቤት የመሥሪያ ቦታው የይዞታ ማስረጃ " በሚመለከተው አካል እንዳይሸጥ፣ እንዳይለወጥ " እንደሚታገድ ረቂቁ ይገልጻል።

ቤት ቀድመው በሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ እነዚህ አስገዳጅ አሠራሮች የተቀመጡት " ደንበኞች የሚደርስባቸውን እንግልት እና ኪሳራ ለመቀነስ በማሰብ " እንደሆነ የአዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል።

ረቂቅ አዋጁ በሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ሌሎችንም ግዴታዎች ጥሏል።

በረቂቁ መሠረት፤ የሪል ስቴት አልሚዎች ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ተከልክለዋል።

" ያለደንበኛው ፍላጎት እና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ አይችልም " ይህንን ለማድረግ በቅድሚያ ደንበኛው መስማማት እንዳለበት ያመለክታል።

ሪል ስቴት አልሚዎች ቤት ገዢዎችን መመመዝገብ እና ቅድመ ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉበት ጊዜም ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦበታል።

አልሚዎች ምዝገባ ማድረግ እና ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉት " የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከተረከቡ " በኋላ ነው።

" በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም " የሚለውም ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ከተቀመጡት ግዴታዎች መካከል ነው።

ለሪል ስቴት ልማት አሠራር የሚዘረጋው አዲሱ አዋጅ፤ ከግዴታዎች ባሻገር አልሚዎች ከመንግሥት " መሬት በስፋት " ማግኘት የሚችሉበትን ሂደትም ያስቀመጠ ነው።

ከመንግሥት መሬት " በስፋት " የሚቀርብላቸው አልሚዎች ረቂቁ ላይ ከተጠቀሱ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ቢያንስ አንዱን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል በብዛት ቤቶችን መገንባት እና ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ " 40 በመቶውን ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ " ማድረግ የሚለው አንዱ ነው።

ይህንን ቅድመ ሁኔታ የሚከተሉ አልሚዎች የሚገነቡበት ቤት ብዛት " እንደ ከተሞች ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 5 ሺህ " ሊሆን እንደሚችል በረቂቁ ላይ ተጠቅሷል።

መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ መሬት " በስፋት " የሚያቀርበው " በአዲስ አበባ ከ5 ሺ በላይ ቤት ለሚገነባ እና ለሚያስተላልፍ " አልሚ እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።

በሌሎች ከተሞች መሬት " በስፋት " የሚቀርበው እደሚኖራቸው " ተጨባጭ የቤት ፍላጎት " ሲሆን፣ " ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባሉ ከተሞች " ደግሞ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶችን ለሚገነቡ አልሚዎች እንደሚቀርብላቸው ረቂቁ ያስረዳል።

ከመንግሥት መሬት " በስፋት " ማግኘት የሚፈልጉ አልሚዎች የተቀመጠባቸው ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከውጭ ምንዛሬ ጋር የተገናኙ ናቸው።

በአገር ውስጥ " በጥራት እና በብዛት የማይገኙ " ግብአቶችን በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (ፍራንኮ ቫሉታ) የሚያስገቡ እንዲሁም የሚያገኙትን ትርፍ እስከ አስር ዓመት ከአገር ሳያወጡ አገር ውስጥ መልሰው የሚጠቀሙ አልሚዎች የዚህ አሠራር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።

" የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይት እና ግመታ " የተሰኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተጨማሪ ዕይታ ወደ ከተማ፣ መሠረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መርቶታል።

መረጃው ከቢቢሲ አማርኛ የተወሰደ ነው።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

08 Oct, 19:29


የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ።

ከመስከረም 28/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በሥራ ላይ የሚቆይ የሁሉም የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉ ተሰምቷል።

በዚህ መሰረት፦
➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር
➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር
➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር 97.67 በሊትር 
➡️ የአውሮፕላን ነዳጅ - ብር 77.76 በሊትር ሆኗል።

መረጃው ከንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነው የተገኘው።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

03 Oct, 06:16


አመታዊውን የእንስሳት እርባታ አውደርዕይ እና ጉባኤ ለመቀላቀል ዝግጁ ነዎት?

የኢትዮጵያ የእንስሳት እርባታ አውደርዕይ እና ጉባኤ ከጥቅምት 21 - 23 በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፣ እርስዎም በዚህ አውደርዕይ ላይ ከተጋበዙ የዘርፉ ሁነኛ ተዋናዮች ፣ ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ላይ ከተሰማሩ ባለሙያዎች ጠቃሚ ልምድ ያገኛሉ።

ከጥቅምት 21 - 23 በሚሊኒየም አዳራሽ አይቀርም!!!

ለመጎብኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://bit.ly/EAPEvents2024
ለመሳተፍ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://bit.ly/EAPExhibit-2024
ድረ-ገጻችንን ይጎብኙ
www.ethiopoultryexpo.com
ኢሜይል
[email protected]
ስልክ
+251996066631 | +251929308364

#PranaEvents #ALEC #africanlivestock #ALEC2024 #EthiopiaLivestockMarket #LivestockTechnology #goats #SectorGrowth #LivestockIndustry #BusinessGrowth #livestock #NetworkingOpportunities #Cows #Ethiopia #Innovation #Exhibition #LivestockExpo #EastAfrica #Meat #SheepFarming #Sheep

ስለ ስራ!

02 Oct, 15:14


#ኢትዮጵያ

ባንኮች በአገልግሎት ክፍያ ዋጋ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ ጨምረዋል።

በአዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሕግ መሰረት ባንኮች በሚሰጧቸው  አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲጣል ታውጇል፡፡

በዚህም የመንግሥት እና የግል ባንኮች ከመስከረም 21 ቀን 2017 ዓ. ም ጀምሮ በባንክ አገልግሎቶች ላይ በሚከፈል የአገልግሎት ክፍያ ላይ የተጨማሪ እሴት ታክስ ታሪፍ ጨምረዋል።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

02 Oct, 14:11


#መረጃ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለአምስት ባንክ ላልሆኑ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች (Forex Bureau) የስራ ፈቃድ ሰጠ!
የውጪ ምንዛሬ ቢሮዎቹ…

ዶላር #መግዛት የሚችሉት (ብር ሰጥተው ዶላር የሚቀበሉት)….
ከማንኛውም ግለሰብ ወይም ድርጅት እስከ 10ሺ ዶላር!

የጉምሩክ ዲክላራሲዮን (ማረጋገጫ ከሚያቀርቡ) የቻሉትን ያህል ዶላር መግዛት ይችላሉ!

ዶላር #መሸጥ የሚችሉት (ብር ተቀብለው ዶላር የሚሰጡት)

ወደውጪ ለመሄድ አስፈላጊውን የጉዞ ሰነድ ለሚያቀርቡ የግል ተጓዦች (ለምሳሌ ቪዛ) እስከ 5ሺ ዶላር ሊሸጡ ይችላሉ!

ለንግድ ስራ ተጓዦች (አስመጪ ሊሆን ይችላል) እስከ 10ሺ ዶላር ሊሸጡ ይችላሉ!

ለንግድ ስራ ተጓዦች (አስመጪ ሊሆን ይችላል) እስከ 10ሺ ዶላር ሊሸጡ ይችላሉ!

source The economics view

ስለ ስራ!

23 Sep, 08:41


የDHL አስገራሚ ታሪክ

"DHL" አድሪያን ዳልሴ፣ ላሪ ሂልብለም፣ ሮበርት ሊን (ADRIAN DALSEY, LARRY HILLBLOM, ROBERT LYNN) የተባሉ ሦስት ወጣቶች በአባቶቻቼው ስም ያወጡት አህጽሮተቃል ነው። እነዚህ ወጣቶች እ.ኤ.አ. በ 1969 በነበራቸው አነስተኛ ገንዘብ ዕቃ የማድረስ ሥራ ጀመሩ። ጠንክረው ለ 55 ዓመታት በመሥራታቸውም ኢንዱስትሪ ላይ ለውጥ አመጡ:: ዛሬ

250 አውሮፕላኖች
32,000 ተሸከርካሪዎች።
550,000 ሠራተኞች አሉት። በአሁኑ ጊዜ DHL በመላው ዓለም ላይ አለ ማለት ይቻላል።

"መልዕቱ ጠንክሮ የሠራ ይሳካለታል" የሚል ነው።
የበለጠ ለመሥራት ተነሳሱ

✍️ Dr Fami