ስለ ስራ!

@selesera


ስራ በእውቀት እንዲሰራ እንተጋለን!
FB - https://www.facebook.com/groups/1153093882014917/?ref=share&mibextid=NSMWBT
Youtube - https://www.youtube.com/@SilSira-zs5rw
Tiktok - tiktok.com/@sile.sira
WhatsApp - https://whatsapp.com/channel/0029Va5Ch0O9WtBw5eGcdZ3H

ስለ ስራ!

21 Oct, 16:41


#ደመወዝ : የደመወዝ ጭማሪ ተፈቅዶና በጀቱም ጸድቆ ክፍያው ከጥቅምት ወር 2017 ዓ.ም.  ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ዛሬ አሳውቋል።

ከገንዘብ ሚኒስቴር የተፈቀደው በጀት፣ የአፈጻጸም መመሪያውንና የክፍያ ትዕዛዙን ለ12ቱ ክልሎች፣ ለሁለቱ የከተማ አስተዳደሮችና ለፌደራል ተቋማት ዛሬ መተላለፉም ተገልጿል።

(ከጥቅምት ወር 2017 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረገው ይፋዊ የደመወዝ ስኬል ከላይ ተያይዟል)

#CivilServiceCommission
#MekuriaHaile

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

18 Oct, 10:42


ከዚህ በፊት የቅዳሜ ውይይታችን ላይ እንግዳ የነበሩት አቶ ኢብራሂም አብዱ የሚከተለውን ሀሳብ በገፃቸው አጋርተዋል
===============
የኢትዬ ቴሌኮም ሼር ልግዛ ወይንስ አልግዛ?

ሼር ለመግዛት ስናሰብ የድርጅቱን አሰተዳደራዊና የፋይናንስ ጤንነት ማረጋገጥ አለብን። የአንድ ድርጅት የፋይናንሰ ጤንነት ለማወቅ መጠናዊ (quantitative)እና አይነታዊ (qualitative) መለኪያዎች አሉ።

✍🏽 ቀዳሚው የድርጅት ፋይናንሰ መጠናዊ መለኪያ አጠቃላይ የገበያ ዋጋ (Market Capitakization) ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ለአክሲዮን ሸያጭ ያወጣው የሸያጭና የድርጅት ቁመና መግለጫ ሪፖርት (prospectus) እንደሚያሳየው የእያንዳንዱ ዋጋ 300 ብር የሆነ አጠቃላይ 1 ቢሊየን ሼሮች አሉት። ይህም ማለት አጠቃላይ የገበያ ዋጋዬ ነው ብሎ ያሰቀመጠው 300 ቢሊየን ብር ነው። ከዚህ ውሰጥ ለሽያጭ የቀረበው እያንዳንዳቸው 300 ብር የገጽ ዋጋ ያላቸው 1 ሚሊየን ሼሮችን ነው። የድርጅቱ አጠቃላይ የገበያ ዋጋ 300 ቢሊየን ነው ስለተባለ ነው ማለት አይደለም። ይሄ የሚያመለክተን የሼሮቹን ዋጋ ወይም በስቶክ ማርኬት ውስጥ የሚኖረውን ዋጋ ነው። የሚጠቅመንም ኢንደስትሪው ውስጥ ካሉ ሌሎች ተመሳሳይ ድርጅቶች ጋር ለማነጻጸር ነው። የድርጅቱን ትክክለኛ ዋጋ የምናውቀው Enterprise value በማሰላት ነው። ይህ በቀላሉ የድርጅቱን የገበያ ዋጋ ላይ ድርጅቱ ያለበትን ብድር በመደመርና ያለውን ጥሬ ገንዘብ በመቀነስ ማስላት ይቻላል። በተጨማሪ አይነታዊ የሆኑ መለኪያዎችን በመጨመር ድርጅቱ ያለውን ሀብት፥ የዘረጋውን መሰረተ ልማት፥ የሰበሰባቸውን ደንበኞች፥ ማፍለቅ የሚችለውን ገቢ፥ የገነባውን ብራንድ፥ በገበያው ውስጥ ያለውን ድርሻ እንዲሁም ያለበትን እዳ ግምት ውስጥ አሰገብተን ማሰላት እንችላለን።

✍🏽 የገቢና የትርፍ (Revenue& Earning)ልኬት ነው። ቢያንሰ ባለፉት አምስት አመታት የድርጅቱ ገቢ ምን ያክል ነበር? በምን ያህል እያደገ ነው? የትርፉ ምጣኔስ? የሚሉ ጥያቄዎችን በማንሳት ማስላትና ሂደቱን መረዳት እንችላለን። ለምሳሌ የኢትዬ ቴሌኮምን የገቢና ትርፍ እድገት ስንመለከት በ 2020 ገቢው 56 ቢሊየን ብር አካባቢ የነበረ ሲሆን በሰኔ 2024 ደግሞ 93•7 ቢሊየን ብር ደርሷል። ይህ በአማካይ የገቢው እድገት 21% አካባቢ እንደሆነ ያሳያል።

✍🏽ሌላው የፋይናንሰ ጤንነት መለኪያ የሼር ገቢ (Earning per share)ነው። በዚ ቀመር የድርጅቱ አንድ ሼር በአመቱ ምን ያክል የትርፍ ምጣኔ አገኘ የሚለው ይሰላል።
ለምሳሌ: ኢትዬ ቴሌ ኮም ባለፈው የሂሳብ አመት የተጣራ ትርፉ  21•79 ቢሊየን ብር እንደሆነ ተገልጽዋል። ይህ ትርፍ ድርጅቱ ላለው አጠቃላይ የሼር ብዛት (1 ቢሊየን) ሲካፈል 21•79 ብር የሼር ገቢ ምጣኔ ይኖረዋል። ይህም ማለት አንድ ሼር 21•79 ብር ትርፍ ይኖረዋል። አሁን ባለው የሼር ዋጋ አንዱ ሼር 300 ብር የሚሸጥ በመሆኑ የ 300 ብር ኢንቨሰትመንት በአመት 22 ብር አካባቢ ትርፍ ያሰገኛል። ይህ ትርፍ ያለፉት አመታት እድገቱን ከተከተለ በየአመቱ በአማካይ 21 ፐርሰንት እያደገ ይሄዳል።

✍🏽ሌላኛውና ወሳኝ የሚባለው የፋይናንሰ መለኪያ PEG ratio ይባላል። የአንድ ሼርን ትርፍ እድገትን ግምት ውስጥ አሰገብተን የምናሰላበትና የሼሩ ዋጋ ተገቢ ነው? በዝቶበታል? ወይንስ ርካሸ ነው የሚል የሚያመላክተን ነው።

የቴሌን ምሳሌ ቀጠለን ብንመለከተው የአንድ ሼር ትርፍ 22 ብር አካባቢ እንደሆነ አይተናል። ይህን የአንድ ሼር ትርፍ ለአመታዊ እድገቱ ማለትም 21 ፐርሰንት (በሙሉ ቁጥር) ሰናካፍለው 1•04 አካባቢ ይመጣል። የአንድ ሼር PEG ratio ከ1 በላይ ከሆነ የሼር መሸጫ ዋጋው ውድ መሆኑን ያመላክታል።

✍🏽ከነዚህ በተጨማሪ ለውሳኔ የሚያግዙን ንፅፅራዊ የሆኑ የፋይናንሰ ጤንነት መለኪያዎች አሉ። ከነዚህ ቀዳሚው የሼር ትርፍ ንጻሬን(EPS ratio) ከሌሎች ትርፎች ጋር ማነጻጸር ነው። ከላይ እንዳየነው የኢትዬ ቴሌኮም የአንድ ሼር ትርፍ 22 ብር አካባቢ ነበር። ይህን ትርፍ በአንድ ሼር መሽጫ ዋጋ ስናካፍለው (22/300)= 7 ፐርሰንት አካባቢ ነው። ሰለዚህም ባለፈው የሂሳብ አመት የቴሌ ሼር የትርፍ ምጣኔ 7 % ብቻ ነበር። ይህ ደግሞ ከባንክ የቁጠባ ወለድ በታች ከመሆኑ በተጨማሪም ከሌሎች ኢንቨሰትመንቶች የትርፍ ምጣኔ ያነስ ነው።

✍🏽 ግምት ውስጥ መግባት ካለበት የአይነታዊ መለኪያ አንዱ የድርጅቱ የቢዝነሰ ሞዴል የእድገት ተስፋ ነው። ኢትዮ ቴሌኮም ከቴሌኮም ሰርቪስ በተጨማሪ ግዙፉ የዲጂታል ፋይናንሰ(Fin-Tech) ተቋም እየሆነ መጥቷል። ይህም የድርጅቱን እድገት ብሩህ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዬ ቴሌኮም ለመሰረተ ልማት ዝርጋታ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ያፈሰሰ በመሆኑ ባለፉት አመታት ትርፉ ያነስ የመሆን እድሉና ወደፊት የማደግ ተሰፋ እንዳለው አመላካች ነው።

✍️የአንድ ድርጅትን ሼር ለመግዛት እነዚህ መለኪያዎች በቂ አይደሉም። ወሳኙ መለኪያ መግዛት የፈለግንበት ምክኒያት ነው።  ከትርፍ ባሻገር ባለቤት የመሆን፥ ተጽዕኖ የመፍጠር፥ ውርስ የመሳሰሉ ምክኒያቶች ሊኖሩን ይችላሉ። ሌላው እጃችን ላይ ያለው የገንዘብ መጠንና ያሉን አማራጭ ኢንቨሰትመንቶች ውሳኔያችን ላይ ተፅዕኖ ያሳድራል።

ስለ ስራ!

18 Oct, 06:08


"የኢትዮ ቴሌኮምን ሼር እንግዛ ወይ?"

ታዋቂው የንግድ አማካሪ እና አሰልጣኝ ጌቱ ከበደ በማህበራዊ ሚድያ አድራሻቸው የሚከተለውን አስፍረዋል።
=========================

"የኢትዮ ቴሌኮምን ሼር እንግዛ ወይ?"

ይህ የብዙዎች ጥያቄ ነው። የዚህ ዓይነት ጥያቄ ከሀገር ውስጥም ከውጭ ሀገርም በውስጥ በኩል እየቀረበልኝ ነው። በተመሳሳይ ለአንዳንድ ወዳጆቼም እንዲህ ዓይነት ጥያቄ እንደቀረበላቸው እገምታለሁ።

ለእንደዚህ ዓይነት ጥያቄ "ግዙ" ማለትም "አትግዙ" ማለትም ተገቢ አይሆንም። ምክንያቱም ብዙ የማይታወቁ መረጃዎች ስላሉ ነው።

ለእያንዳንዱ ግለሰብ ውሳኔ እንዲረዳ ግን አንዳንድ ነጥቦችን ማየት ይጠቅማል።

፩) አብዛኛው አክሲዮን የተያዘው በማን ነው?

ከ20-25 % በላይ የሚሆነው አክሲዮን በ1 አካል ከተያዘ ትኩረትን የሚስብ ነው። በ1 አካል የተያዘው አክሲዮን ከ33% በላይ ከሆነ ደግሞ አሳሳቢ ነው። 50% በላይ ከሆነ ደግሞ ያንን አክሲዮን መግዛት አደገኛ ነው። ከ75% በላይ አክሲዮን በ1 አካል ከተያዘ ደግሞ የተለየ ምክንያት ከሌለህ እና አክሲዮን ሻጩን በጣም የምታምነው ካልሆነ በቀር አክሲዮን የምትገዛበት ልዩ ምክንያት ያስፈልግሃል።

ምክንያቱም ባለ ብዙ አክሲዮኑ በፈለገ ጊዜ አክሲዮን እያወጣ እየሸጠ ያንተን ድርሻ ያመነምነዋል። ይህ Dilution (ማቅጠን) ይባላል። ለምሳሌ : 1% ቢኖርህ ባለ ትልቅ አክሲዮኑ አዲስ አክሲዮን በመሸጥ ድርሻህን ወደ 5% ሲለው ደግሞ ወደ 0.5% ያወርደዋል። አንተም እያየኸው ሼርህ ይሟሟል። ብር ምንዛሪው ሲቀንስ አላየህም? እያየኸው ዓቅሙ አልላሸቀም? እንደዚያ ማለት ነው።

ECX ላይ መጀመሪያ ወንበር ሲሸጥ ለ100 ገዢዎች ብቻ ተብሎ ነበር የተሰበከው። በኋላ ግን ያለገዢዎች ምክክር ወደ 400 አደገ። አሁን ስንት እንደሆኑ አኣውቅም። በንግድ ስትሻረክ መተማመን ወሳኝ ጉዳይ ነው።

አንድ 3/4ኛ ድርሻ ያለው አካል ካለ፣ ውሳኔው በሙሉ በእርሱ ቁጥጥር ስር ነው። ያ ችግር የማይኖረው፣ ውሳኔ ሰጪው አንድም ታማኝ ሲሆን፣ ሲቀጥልም አንተ ሌላ አማራጭ ሳይኖርህ ቀርቶ ይህ እድል በልዩነት ሲሰጥህና አንተም ተስፋ ስታደርግበት ነው።

የኢትዮቴሌኮም ኢንዱስትሪ አሁን ባለው ሁኔታ አትራፊ ነው። አትራፊ መሆኑ ብቻ ግን አዋጭ ኢንቨስትመንት ነው ማለት አይደለም። ሌሎች መታየት ያለባቸው ጉዳዮች ይኖራሉ።

አሁን በተነገረው መሠረት መንግስት 90% ድርሻን ይዞ 90% ለሌሎች የሚሸጥ ነው። የመንግስት ድርሻ ከ30% ባይበልጥ ግሩም ነበር።

የባለቤቱ (የመንግስት) ታማኝነት ዋናው ጉዳይ ነው። አሁን ባለው የ90% አክሲዮን ድርሻ ሁኔታ መንግስት ሌሎች ባለአክሲዮኖችን ሳያወያይ ዋና ዋና ጉዳዮችን መቀየር የሚያስችል መብት ህጉ ይሰጠዋል። አንተ ባለ ትንሽ አክሲዮኑ የተባለውን ከመቀበል ውጪ መብት የለህም።

የምታምነውና በጥሩ % ትርፋማ የሆነ እና በየዓመቱ ትርፍ የሚያከፋፍል አክሲዮን ሻጭ ካገኘህ ግን 0.001% ድርሻም ትልቅ ነውና ብትገዛ ጥሩ ነው።

ባለ ትልቅ አክሲዮኑ ፈቃደኛ ካልሆነ ግን ድርጅቱ አትርፎም ትርፍ እንዳይከፋፈል ሊወስን ይችላል። አንተም ሁሌ ወሬህ አክሲዮን አለኝ ከማለት ባለፈ "ላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም እላይ" እያልህ መክረም ነው። እንደዚያ የሆኑ ብዙ የሀገራችን አክሲዮኖች አሉ።

መንግስት "ቴሌ የምትታለብ ላም ናት" ሲል ከርሞ አሁን ለምን አክሲዮኑን ይሸጣል? የዚህ ምክንያት እንደየአመለካከታችን ይለያያል። ዋናው ምክንያት የሚመስለኝ የገንዘብ ግሽበትን ለመቆጣጠር ገበያ ውስጥ ያለውን ብር መምጠጥ ነው። ይሄ በታክስ፣ ቅጣት እና የመንግስት አገልግሎቶች ዋጋ መናር የታየ ነው።

መንግስት እያደረገ ያለው ነገር ሲታይ ለዜጎች ትርፍ ማጋራት አስቦ አይመስልም። ይልቅስ ተቀማጭ ገንዘብ ካላቸው ግለሰቦች ላይ ገንዘባቸውን መምጠጥ ይመስላል። አይደለም ያላችሁም ልክ ትሆኑ ይሆናል። ለእኔ የታየኝ ግን እንዲያ ነው።

፪)

፫)

፬)

ብዬ የማቀርባቸው ሌሎችም ማብራሪያዎች ነበሩኝ። ግን ምን አስጨነቀኝ? ለገባው ይሄው 1 ምክንያት በቂ ነው።

ውሳኔውን ግን በራሳችሁ ወስኑ።

ስለ ስራ!

15 Oct, 12:04


አዲሱን የብሔራዊ ባንክ መመሪያ ተከትሎ ባንኮች በውጭ ምንዛሬ ላይ እስከ አስራ አንድ ብር የሚደርስ ቅናሽ ማሳየታቸው ተገለጸ

ማክሰኞ ጥቅምት 05 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ) ብሄራዊ ባንክ አዲስ ባወጣው መመሪያ ባንኮች በየቀኑ በሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ የመሸጫና የመግዣ መጠን ላይ ልዩነቱ ከሁለት በመቶ በላይ እንዳይሆን ማስታወቁን ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የዶላር መሸጫ ዋጋቸው ላይ ቅናሽ አሳይተዋል፡፡

በዚህ የግብይት ሂደት ውስጥ ያሉ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ የመሸጫ እና የመግዣ ዋጋቸውን በየዕለቱ እየወሰኑ ይፋ ሲያደርጉ የቆዩ ሲሆን፣ በአብዛኛዎቹ ባንኮች በዶላር መግዣ እና መሸጫ ዋጋቸው መካከል ያለው ልዩነት ከ10 በመቶ በላይ መድረሱ ተጠቁሟል።

በመሆኑም ብሔራዊ ባንክ ከዛሬ ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆን ባስተዋወቀው አዲስ ፖሊሲ ባንኮች በውጭ ምንዛሪ የመግዣ እና የመሸጫ ዋጋ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ መብለጥ እንደሌለበት ወስኗል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2017 ባወጣው ዕለታዊ የውጭ ምንዛሬ ግብይት የዋጋ ዝርዝር ላይ የዶላር የመሸጫ ዋጋው ከትናንቱ ጋር ሲነጻጸር የስምንት ብር ቅናሽ ያሳየ ሲሆን የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ደግሞ የአስራ አንድ ብር ቅናሽ አድርጓል፡፡

ብሔራዊ ባንክ አዲሱን መመሪያ በተመለከተ ለሁሉም ባንኮች በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን እስከ ረቡዕ ድረስ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አዟል።

ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ

ስለ ስራ!

15 Oct, 11:55


ባንኮች የውጭ ምንዛሬን የሚገዙበትና የሚሸጡበት የልዩነት መጠን ከ2 በመቶ እንዳይበልጥ የሚገድብ መመሪያ ይፋ ሆነ፡፡

ማክሰኞ ጥቅምት 05 ቀን 2016(አዲስ ማለዳ)ብሄራዊ ባንክ አዲስ ያወጣው መመሪያ ባንኮች በየቀኑ በሚያወጡት የውጭ ምንዛሬ የመሸጫና የመግዣ መጠን ላይ ልዩነቱ ከሁለት በመቶ በላይ እንዳይሆን የሚገድብ እንደሆነም አስታውቋል፡፡

ለሙሉ ዘገባ፡ https://addismaleda.com/archives/39311

ስለ ስራ!

15 Oct, 08:42


የስለስራ! እንግዳችን የነበሩት አቶ ሙከሚል በድሩ በቅርቡ ንግድ ባንክ ያዘጋጀሁትን የውጭ ምንዛሬ ነጋዴዎች አልተጠቀሙትም ማለቱን ተከትሎ ለምን ይህ እንደተፈጠረ ያብራሩበትን ምስል አጋርተናችኋል!

ስለ ስራ!

12 Oct, 17:09


የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት
ግብይትና ግመታ ረቂቅ አዋጅ አጭር ማብራሪያ

ስለ ስራ!

11 Oct, 03:25


#ሪልስቴት

ያልተገነባ ቤት / ግንባታ ከማከናወናቸው በፊት ቤት የሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ በዝግ አካውንት እንዲያስቀምጡ ሊገደዱ ነው ፤ በተጨማሪ ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ሊከለከሉ ነው።

ይህንም የሚመለከት ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ዛሬ ቀርቧል።

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ምን ይላል ?

ቤት ለመገንባት የመሬት የይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ያላገኙ የሪል ስቴት አልሚዎች ደንበኞችን #እንዳይመዘግቡ እና #ቅድመ_ክፍያ እንዳይሰበስቡ ይከለክላል።

በአሁኑ ጊዜ ባለው አሠራር መሠረት የንግድ ፈቃድ በማውጣት ብቻ ወደ ሪል ስቴት ገበያው ሲቀላቀሉ የነበሩት አልሚዎች፤ በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ " የብቃት ማረጋገጫ ፈቃድ " የማውጣት ግዴታ ተጥሎባቸዋል። የአገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሀብት ሪል ስቴት አልሚዎች ይህንን ፈቃድ ለማግኘት ቢያንስ 50 ቤቶችን ገንብተው የሚያስከረክቡ መሆን አለባቸው።

የአገር ውስጥ እና የውጭ አልሚዎች ግንባታውን ለማከናወን የሚያስፈልገውን " የፋይናንስ አቅርቦት ምንጭ " የማቅረብ ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦባቸዋል። ይሁንና ረቂቁ፤ " የቅድሚያ ቤት ሽያጭ ተጠቃሚነት " መብትን ከቅድመ ሁኔታ ጋር ለአገር ውስጥ ባለሀብቶች ሰጥቷል።

ይህ አሠራር የሪል ስቴት አልሚዎች የቤት ግንባታውን ሳያከናውኑ ወይም በሂደት ላይ እያለ ለግንባታው የሚውልን ፋይናንስ የሚያሰባስቡበት እና ገንዘቡብ ለግንባታው የሚያውሉበት መንገድ ነው።

የቤት ግንባታው ሳይከናወን በፊት ከገዢዎች ጋር ውል ማሰር እና ክፍያ መፈጸም ኢትዮጵያ ውስጥ በሪል ስቴት ልማት ላይ በተሰማሩ አልሚዎች በኩል የተለመደ አሰራር ነው።

አዲሱ ረቂቅ አዋጅ፤ በዚህ ዓይነት መልኩ ለግንባታ የሚውለውን ሀብት ማሰባሰብ የሚፈልጉ አልሚዎች " አግባብ ካለዉ አካል ፈቃድ ማቅረብ " ይጠበቅባቸዋል። ይህም ግዴታ ነው።

የቅድመ ሽያጭ ዘዴን መጠቀም የሚፈልጉት ሪል ስቴት አልሚዎች፤ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡት ገንዘብ የሚቀመጥበት የባንክ ሂሳብ እና የገንዘብ አወጣጥ ላይም አስገዳጅ አሠራር በረቂቅ አዋጁ ተጥሎባቸዋል።

አልሚዎቹ ከቤት ገዢዎች የሚሰበስቡትን ገንዘብ " የዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ ማደረግ ወይም ማስያዝ " እንዳለባቸው ረቂቅ ሕጉ ላይ ሰፍሯል።

አዲሱ ሕግ፤ ገንዘቡ የሚቀመጥበት ዝግ የባንክ አካውንት የሚከፈተው " አግባብ ባለው አካል ፈቃድ መሠረት " እንደሆነም ያስረዳል።

በዝግ የባንክ ሂሳብ ገቢ የተደረገው ገንዘብ የሚለቀቅበት ሁኔታ ከረቂቅ አዋጁ መፅደቅ በኋላ በሚወጣ ደንብ ይወሠናል።

ከዚህም ባሻገር በቅድሚያ የተሸጠው ቤት ተገንብቶ ለተጠቃሚዎች እስከሚተላለፍ ድረስ የቤት የመሥሪያ ቦታው የይዞታ ማስረጃ " በሚመለከተው አካል እንዳይሸጥ፣ እንዳይለወጥ " እንደሚታገድ ረቂቁ ይገልጻል።

ቤት ቀድመው በሚሸጡ ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ እነዚህ አስገዳጅ አሠራሮች የተቀመጡት " ደንበኞች የሚደርስባቸውን እንግልት እና ኪሳራ ለመቀነስ በማሰብ " እንደሆነ የአዋጁ ማብራሪያ ያስረዳል።

ረቂቅ አዋጁ በሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ሌሎችንም ግዴታዎች ጥሏል።

በረቂቁ መሠረት፤ የሪል ስቴት አልሚዎች ግንባታው 80 በመቶ ላይ ያልደረሰን ቤት ለደንበኞች እንዳያስተላልፉ ተከልክለዋል።

" ያለደንበኛው ፍላጎት እና ፈቃድ አጠቃላይ ግንባታው ቢያንስ 80 በመቶ ያልተጠናቀቀ ቤት ለደንበኞች ሊያስተላልፍ አይችልም " ይህንን ለማድረግ በቅድሚያ ደንበኛው መስማማት እንዳለበት ያመለክታል።

ሪል ስቴት አልሚዎች ቤት ገዢዎችን መመመዝገብ እና ቅድመ ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉበት ጊዜም ቅድመ ሁኔታ ተቀምጦበታል።

አልሚዎች ምዝገባ ማድረግ እና ክፍያ መሰብሰብ የሚችሉት " የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ እና የግንባታ ፈቃድ ከሚመለከተው አካል ከተረከቡ " በኋላ ነው።

" በሕጋዊ መንገድ የተረከበው መሬት ሊያስተናግድ ከሚችለዉ የቤት ደንበኛ በላይ መመዝገብ አይችልም " የሚለውም ሪል ስቴት አልሚዎች ላይ ከተቀመጡት ግዴታዎች መካከል ነው።

ለሪል ስቴት ልማት አሠራር የሚዘረጋው አዲሱ አዋጅ፤ ከግዴታዎች ባሻገር አልሚዎች ከመንግሥት " መሬት በስፋት " ማግኘት የሚችሉበትን ሂደትም ያስቀመጠ ነው።

ከመንግሥት መሬት " በስፋት " የሚቀርብላቸው አልሚዎች ረቂቁ ላይ ከተጠቀሱ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎች ውስጥ ቢያንስ አንዱን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።

ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች መካከል በብዛት ቤቶችን መገንባት እና ከእነዚህ ቤቶች ውስጥ " 40 በመቶውን ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ላላቸው የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ " ማድረግ የሚለው አንዱ ነው።

ይህንን ቅድመ ሁኔታ የሚከተሉ አልሚዎች የሚገነቡበት ቤት ብዛት " እንደ ከተሞች ደረጃ በአንድ ጊዜ ከ500 እስከ 5 ሺህ " ሊሆን እንደሚችል በረቂቁ ላይ ተጠቅሷል።

መንግሥት በአዲስ አበባ ከተማ መሬት " በስፋት " የሚያቀርበው " በአዲስ አበባ ከ5 ሺ በላይ ቤት ለሚገነባ እና ለሚያስተላልፍ " አልሚ እንደሆነ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።

በሌሎች ከተሞች መሬት " በስፋት " የሚቀርበው እደሚኖራቸው " ተጨባጭ የቤት ፍላጎት " ሲሆን፣ " ኢንዱስትሪ ፓርክ ያለበት አካባቢ ባሉ ከተሞች " ደግሞ ከአንድ ሺህ በላይ ቤቶችን ለሚገነቡ አልሚዎች እንደሚቀርብላቸው ረቂቁ ያስረዳል።

ከመንግሥት መሬት " በስፋት " ማግኘት የሚፈልጉ አልሚዎች የተቀመጠባቸው ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ከውጭ ምንዛሬ ጋር የተገናኙ ናቸው።

በአገር ውስጥ " በጥራት እና በብዛት የማይገኙ " ግብአቶችን በራሳቸው የውጭ ምንዛሬ (ፍራንኮ ቫሉታ) የሚያስገቡ እንዲሁም የሚያገኙትን ትርፍ እስከ አስር ዓመት ከአገር ሳያወጡ አገር ውስጥ መልሰው የሚጠቀሙ አልሚዎች የዚህ አሠራር ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ረቂቁ ላይ ሰፍሯል።

" የሪል ስቴት ልማት እና የማይንቀሳቀስ ንብረት ግብይት እና ግመታ " የተሰኘው ይህ ረቂቅ አዋጅ የቀረበለት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለተጨማሪ ዕይታ ወደ ከተማ፣ መሠረተ ልማት እና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በሙሉ ድምፅ መርቶታል።

መረጃው ከቢቢሲ አማርኛ የተወሰደ ነው።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

08 Oct, 19:29


የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ።

ከመስከረም 28/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ በሥራ ላይ የሚቆይ የሁሉም የነዳጅ ውጤቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ መደረጉ ተሰምቷል።

በዚህ መሰረት፦
➡️ ቤንዚን - ብር 91.14 በሊትር
➡️ ነጭ ናፍጣ - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ኬሮሲን - ብር 90.28 በሊትር
➡️ ቀላል ጥቁር ናፍጣ - ብር 100.20 በሊትር
➡️ ከባድ ጥቁር ናፍጣ - ብር 97.67 በሊትር 
➡️ የአውሮፕላን ነዳጅ - ብር 77.76 በሊትር ሆኗል።

መረጃው ከንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ነው የተገኘው።

@tikvahethiopia

ስለ ስራ!

03 Oct, 06:16


አመታዊውን የእንስሳት እርባታ አውደርዕይ እና ጉባኤ ለመቀላቀል ዝግጁ ነዎት?

የኢትዮጵያ የእንስሳት እርባታ አውደርዕይ እና ጉባኤ ከጥቅምት 21 - 23 በሚሊኒየም አዳራሽ ይካሄዳል፣ እርስዎም በዚህ አውደርዕይ ላይ ከተጋበዙ የዘርፉ ሁነኛ ተዋናዮች ፣ ከሚመለከታቸው የመንግስት ተቋማት እንዲሁም በእንስሳት እርባታ ዘርፍ ላይ ከተሰማሩ ባለሙያዎች ጠቃሚ ልምድ ያገኛሉ።

ከጥቅምት 21 - 23 በሚሊኒየም አዳራሽ አይቀርም!!!

ለመጎብኘት ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://bit.ly/EAPEvents2024
ለመሳተፍ ማስፈንጠሪያውን ይጫኑ
https://bit.ly/EAPExhibit-2024
ድረ-ገጻችንን ይጎብኙ
www.ethiopoultryexpo.com
ኢሜይል
[email protected]
ስልክ
+251996066631 | +251929308364

#PranaEvents #ALEC #africanlivestock #ALEC2024 #EthiopiaLivestockMarket #LivestockTechnology #goats #SectorGrowth #LivestockIndustry #BusinessGrowth #livestock #NetworkingOpportunities #Cows #Ethiopia #Innovation #Exhibition #LivestockExpo #EastAfrica #Meat #SheepFarming #Sheep

6,369

subscribers

142

photos

2

videos