Ismaiil Nuru

@ismaiilnuru


ዘመንን እናሰልማለን እንጅ ኢስላምን አናዘምንም!
ሀሳብ/አስተያየት፦ @Ismaiilnuru_Bot

Ismaiil Nuru

20 Oct, 17:00


በሌሎች ሶሻል ሚዲያዎች ላይ ለማጋራት ይህን የምስል ጥራት ፋይል ያውርዱ!

Ismaiil Nuru

14 Oct, 19:52


በሌሎች ሶሻል ሚዲያዎች ላይ ለማጋራት ይህን የምስል ጥራት ፋይል ያውርዱ!

Ismaiil Nuru

13 Oct, 18:25


አላህ ሙስሊም እህቶቻችንን ይምራቸው! እኛንም አጋዦች ያድርገን!

Ismaiil Nuru

13 Oct, 15:53


ዋጋህን ባያውቁልህ ልታዝን አይገባም ፤ ሙሉ የአንድ መንደር ህዝብ ዋጋቸውን ባለማወቁ ለሙሳና ለኸድር (ዐለይሂመሰላም) በሩን መክፈት አልፈቀደም ነበር ... አላህ ዘንድ ለሚኖርህ ዋጋ ትጋ! ሰዎችን እርሳቸው! የድብቅ ዒባዳዎችን አብዛ!
(ከፌስቡክ የዐረብኛ ፖስት የተተረጎመ)
የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

Ismaiil Nuru

12 Oct, 21:40


የ ሁዳ እና ሺዐን ምን ያመሳስላቸዋል?

የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

Ismaiil Nuru

12 Oct, 21:37


በሌሎች ሶሻል ሚዲያዎች ላይ ለማጋራት ይህን የምስል ጥራት ፋይል ያውርዱ!

Ismaiil Nuru

11 Oct, 15:04


       °•ምክር ቢጤ ለሰለምቴ እህቶች °•

1) ስላሰለመሽ ብቻ አታግቢው ፦ ስላሰለመሽ ዲንን ያውቃል፣ ስነምግባሩ የተስተካከለ ነው ማለት አይደለም።
ለትዳር ደግሞ በወንድ ልጅ ላይ ሁለቱ የሚፈለጉ መስፈርቶች ናቸው። ስለሆነም ስላሰለመኝ አምነዋለሁ በሚል እሳቤ ከማግባት ተጠንቀቂ።

2) እንደሰለምሽ ቶሎ አታግቢ ፦ ከሰለምሽ በኋላ ትልቁና የመጀመሪያ ስራሽ ዲንን ማወቅ ማንበብና መማር ይሁን። ያኔ ምናልባትም የኢስላም አካል የሚመስሉሽ ግን ያልሆኑ ጉዳዮች ካሉ ይገለጡልሻልና።በኢስላም ስለሴት ልጅ የተደነገጉ ብይኖች ላይ የሚያጠነጥኑ የዲን እውቀት ዘርፎች ላይ ተሳተፊ።

3) የሒጃብ ጓደኛ ትኑርሽ፦ ሸሪዐዊ ሒጃብን ጠንቅቃ የምትለብስ ባለትዳር ጓደኛ ትኑርሽ።የትዳር ጥያቄዎች ሲመጡ የምታማክሪያት ትሁን።

4) ቤተሰቦችሽ ይወቁ ፦ ከሰለምሽ በኋላ በዲኑና በአኽላቁ መልካም ሰው ከገጠመሽና ከተስማማሽ ቤተሰብ ባንቺ እምነት ላይ ባይሆኑም ማሳወቅና ማሳመን ያስፈልጋል።

ትዳር የዘር ሰንሰለት የሚፈጠርበት ተቋም እንደመሆኑ እናትነቱና አባትነቱ መኖሩ ግዴታ ስለሆነ የቤተሰብ ጉዳይነቱ ግልፅ ነው። በኋላም ተያይዘው የሚመጡ ጉዳዮች እነርሱ ጋር የሚደርሱ እንደመሆናቸው ቤተሰቦችሽን አሳውቂ።

5) ዳዒያ ከመሆን ተጠንቀቂ ፦ አሁን ላይ እንደፋሽን የተያዘ ዳዕዋ ላይ ከመሳተፍ ራስሽን ጠብቂ። ዛሬ ተሰልሞ ነገ ሚዲያ ላይ ዳዒ የሚኾንበት ስርአት በኢስላም የለም።ዲን በእውቀት ላይ መጣራት ስለሆነ ፊትሽን ወደ እውቀት አዙሪ።

6) ለትዳር የጠየቀሽን ሰው አጥኚ፦ ቤተሰቡን፣ አኗኗሩን ታሪኩን የማጥናትና የመጠየቅ መብት አለሽ።በዲኑ ጠንካራና መልካም ሰለምቴ ካገኘሽ ለጋራ የስነ ልቦና መናበብ በላጭ ስለሆነ አግቢ።ካልሆነም ጥሩ አኽላቅና ዲን ያለው በኢስላም ላይ ያደገን አግቢ።

7) ቃዲ ምረጪ(ጡ) ፦ ወሊይ የሌላት ሰለምቴ ወሊዩዋ ቃዲ መሆኑ ግልፅ ነው።ስለሆነም ቃዲው ኒካህ ከማሰር በዘለለ  የወሊይነት ሚናውን የሚወጣ የሱና ሰው መሆኑን ማየት የግድ ነው። ሰዎች የሚያውቁት፣  ተሰሚ ሸይኽ ዘንድ ሄዳችሁ ኒካህ አድርጉ። አለመግባባት ቢኖር ጥፋተኛውን ተው የሚል የሚገስፅ ይሆናል።በባል መበደል ቢኖር (ብዙ ጊዜ የሚከሰት እንደመሆኑ) በአላህ የሚወቅስ ቃዲ (ወሊይ) መሆን ይኖርበታልና።

(ብዙ ጊዜ እነዚህ ጉዳዮች ላይ ሰለምቴ እህቶቻችን ጋር   ልብ እንደማይባሉ ስላየሁ ነው። ተጨማሪ ካለ ጨምሩበት ።)

የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

Ismaiil Nuru

08 Oct, 09:25


«አክብሩልን መች አልን?»

ሌላኛው ሚዛናዊ መሳይ ኢሬቻ ከኢስላም የሚያስወጣ ተግባር መሆኑ ሲፃፍና ሲነገር መሀል ሰፋሪ ለመምሰል «ለምን በዚህ ደረጃ ይጮሃል?» «አክብሩልን ያለ የለም!» «ባህሌ ነው ያለ ያክብር የኔ አይደለም ያለ አያክብር» በማለት ሲከላከል እያየን ነው።

ሌላውን ትተን እዚህ ላይ ብቻ መልስ ለመስጠት ያህል ፦

ከ «አክብሩልን» በላይም «አክብሩ» እየተባለ ነው። ለምሳሌ አንድ የክርስትና በአል ላይ ለታቦት ማሳለፊያ የምንጣፍ አምጣ የበአሉን ባንድራ ስቀል
አይነት ትእዛዝ ቢመጣ በቀጥታ ትርጉሙ በአሉን አክብር ማለት ነው።

በተመሳሳይም ለኢሬቻ ይሰራል።ለኢሬቻ የዳቦ አምጣ የውሃ አምጣ የዋቃን ባንድራ ስቀል እያሉ ቢሮክራሲያዊ የማስፈራሪያ ቃላትን መጠቀም በአሉን አክብር ማለት እንጅ ምን ማለት ነው? ከዚያም አልፎ «ይህ ባንድራ የብሄር ሳይሆን የእምነት ባንድራ ነው» እየተባለ በት/ት ቤት ደረጃ እየተሰበከ እያየን እንዴት ነው አክብሩልን መች አልን የሚባለው?

እንደ ሙስሊም በየትኛውም በአሎቻችን ላይ ማንም የሌላ እምነት ተከታይ የኛን በአል እንዲያከብር አናስገድድም መገለጫዎቻችን በማንም ግድግዳ ላይ አንሰቅልም።ምክንያቱም በአሉ የኛ እንጅ የሌሎች ስላልሆነ።

አምላኬ ጥቁር ነው ብሎ የማያምንን ሙስሊም የዋቃ ጉራቻን ባንድራ ስቀል ማለት አክብሩልን ማለት ሳይሆን አክብር! ብሎ ማስገደድ ካልሆነ ማስገደድ የምትሉት እንደ ቢላል አንገታችን ላይ ገመድ ታስሮ ስንገተት ይሆን?

ትናንሽ አንቆቅልሾችን የማንረዳ ጩጬ አድርጋችሁማ አታስቡን እንጅ?

ማስታወሻ ፦ እያወራሁ ያለሁት ስለ ሀይማኖት እንጅ ስለ ብሄር ፖለቲካ አይደለም!

የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

Ismaiil Nuru

06 Oct, 20:40


لا إِلَٰهَ إِلَّا أَنتَ سُبْحَانَكَ إِنِّي كُنتُ مِنَ الظَّالِمِينَ

Ismaiil Nuru

06 Oct, 20:39


በሌሎች ሶሻል ሚዲያዎች ላይ ለማጋራት ይህን የምስል ጥራት ፋይል ያውርዱ!

Ismaiil Nuru

06 Oct, 11:20


ከነዚህ ሰዎች እምነት አንፃር አቡ ጀህል «ረዲየላሁ ዐንሁ»  የሚባልለት አይነት ሰው ነው። አላህ ረሱል (ሰዐወ) የመጡበትን የቁረይሽ ህዝብ በፈጣሪነቱ እንደማይጠራጠር  ሲገልፅ እንዲህ ይላል፦

((وَلَئِن سَأَلْتَهُم مَّنْ خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ لَيَقُولُنَّ اللَّهُ))
“ሰማያትንና ምድርን የፈጠረ ማን እንደ ኾነ ብትጠይቃቸው «አላህ ነው» ይሉሃል”
(አዝዙመር 38 )

እነ አቡጀህል አላህ ምድርን ያነጠፈ፣ ሰማይን የዘረጋ ጌታ መሆኑን አውቀው ሙሽሪክ ያሰኛቸው በአምልኮቱ ላይ ሌሎችን ማጋራታቸው ነው። ይሄ የኢራን መጁሳ ደግሞ ዐሊይ ምድርና ሰማይን ዘርግቷል እያለ ነው።
ዑዝር ይኖረው ይሆን? 

የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

Ismaiil Nuru

05 Oct, 19:39


ኢብኑ ተይሚያህ እንዲህ ይላሉ፦ «ልክ እንዲሁ ቂ ሉ ሚንስተራቸውና  ረሺድ ተብሎ የሚታወቀው ግለሰብ .... ይህ ቆ  ሻ  ሻ፣ ጠ  ማማ፣ ሙ/ ና   ፊ  ቅ የሆነ ሚንስትራቸው ድርሳን አዘጋጅቶ ነበር። ጭብጡም ነብዩ  የየሁዳዎችንና የክርስቲያኖችን ሃይማኖት ወድዷል፣ እነርሱ እምነታቸው አይወገዝባቸውም አይወቀሱም እምነታቸውን ከመፈፀም አይከለከሉም  እንዲሰልሙ አይታዘዙም፣ የሚል ነው። ይህ ቆ   ሻ!ሻ ማስረጃ ያደረገውም “በላቸው «እናንተ ከሓዲዎች ሆይ! ያንን የምትግገዙትን (ጣዖት አሁን) አልግገዛም፡፡ እናንተም እኔ የምግገዛውን (አምላክም አሁን) ተገዢዎች አይደላችሁም፤እኔም ያንን የተገዛችሁትን (ወደፊት) ተገዢ አይደለሁም፣እናንተም እኔ የምግገዛውን (ወደፊት) ተገዢዎች አይደላችሁም፤ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ”  ን ነበር። »

ይህችም አንቀፅ እርሳቸው(መልእክተኛው) የነርሱን እምነት እንደሚወድ ታስይዛለች ብሎ ሞገተና ይህች አንቀጽ ያልተሻረች ሙሕከም ነች በዚህም ብዙ ነገር ተተግብሯል  አለ። የሚታወቀው ነገር እርሱ አላዋቂ መሆኑ ነው። “ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ”  የሚለው የአላህ ቃሉ በርሱ ውስጥ የካ  ፊ/ሮች ሃይማኖት ሐቅና የተወደደ መሆኑን አያስፈርድም።ከነርሱ ሃይማኖት መጥራራትን ነው የሚያመለክተው።ለዚህም የአላህ መልእክተኛ  ምእራፏን አስመልክተው “እርሷ ከሽርክ መጥራሪያ ነች” ብለዋል።»
«አልፈታወል ኩብራ 3/544 »
ምንጭ ፦ ዲሞክራሲና ኢስላም መፅሀፍ

የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

Ismaiil Nuru

05 Oct, 19:39


አብዛኞች ራሳቸውን ወደ ዲን ኢንቲሳብ የሚያደርጉ ሰዎች እንደሚሞግቱት ይህች አንቀፅ ለሙሽሪኮች በሽርካዊ ሃይማኖታቸው ላይ እውቅና መስጠትን ታመላክታለች ብለው ያምናሉ።

የሙሽሪኮች ኢሬቻም የካ ፊ ሮች መስቀልና ሌሎች ክህ ደት ናቸው ማለት እውቅና እንሰጣለን ማለት አይደለም። ሱረቱል ሙቀሽቂሻህ ለሌሎች ሀይማኖቶች እውቅና መስጠትንና የእምነት ነፃነትን የምታፀድቅ አድርጎ ማቅረብ በአቂዳ ላይ ትልቅ ስህተትን መፍጠር ነው።

ይህች ምእራፍ ከክ  ህደት የምታጥራራ (ሙቀሽቂሻህ) ምእራፍ ተብላ የምትታወቅ ሲሆን
የአህሉሱንናህ ወልጀማዐህ ዑለማእ ይህች አንቀፅ ለካ  ፊ  ሮች እውቅና መስጠትን ታመላክታለች ብለው በየትኛውም ቦታ አልተቀበሉም። መዓዘላህ! እንዴት የተውሒድና ከሽርክ የመጥራሪያ የሆነች አንቀፅ ለሽርክ እውቅና ማወጂያ ልትሆን ይችላል?

ኢብኑ ዐባስ ሲናገሩ፦  «በቁርኣን ውስጥ ኢብሊስን በማስቆጣት እንደዚህች አንቀፅ ከባድ የለም። ምክንያቱም እርሷ ተውሒድና ከሽርክ መጥራራት ነችና።» ብለዋል። (አልከሽፍ ወልበያን / ሱረቱል ካ/ፊሩን)

ኢብኑ ተይሚያህ እንዲህ ይላሉ፦ «ለናንተም ሃይማኖታችሁ አለላችሁ ለኔም ሃይማኖቴ አለኝ" ማለት የሚያመላክተው እናንተ በእምነታችሁ ከኔ የተለያችሁ ናችሁ አልጋራችሁም እኔም በእምነቴ የተለየሁ ነኝ በርሱ ውስጥ አትጋሩኝም ማለት ነው ።ልክ “ለእኔ ሥራዬ አለኝ፡፡ ለእናንተም ሠራችሁ አላችሁ፡፡ እናንተ ከምሠራው ነገር ንጹሕ ናችሁ፡፡እኔም ከምትሠሩት ነገር ንጹሕ ነኝ» በላቸው፡፡” [ዩኑስ 41] እንዳለው።»
(  አልጀዋቡ ሰሒሕ ሊመን በድደለ ዲነል መሲሕ)

በድጋሜም  እንዲህ ይላሉ፦ «ይህም (መልእክተኛው) ከነርሱ ሃይማኖት የተጥራራ መሆኑን ያመላክታል።ለዚህም ነው መልእክተኛው  ይህችን ምእራፍ አስመልክተው እርሷ ከሽርክ መጥራራት ነች ያሉት» (  አልፈታወል ኩብራ 3/544)


ኢብኑል ቀይም እንዲህ ይላሉ ፦ «አንቀጿ እንዳሳለፍነው ጥርት ያለን መጥራራትን አስፈርዳለች።(ትርጉሟ) እናንተ ያላችሁበት ሃይማኖት እኛ በርሱ ላይ መቼም አንስማማችሁም፤ እርሱ ከንቱ ሃይማኖት ነው፤ እርሱ የናንተ ብቻ ነው አንጋራችሁም ።እናንተም በኛ በእውነተኛው ሃይማኖት ውስጥ አትጋሩንም ማለት ነው። ይህም የነርሱን እምነት ከመስማማት  የመጥራራትና የመንነጠል  ጣራው ነው።» (ተፍሲር ኢብኒል ቀይም 2/355)

አቡ ሐይያን  እንዲህ አሉ፦ «ለናንተም ሃይማኖታችሁ አለላችሁ ለኔም ሃይማኖቴ አለኝ»ማለት ለናንተ ሽርካችሁ ለኔ ተውሒዴ አለለኝ ማለት ሲሆን ይህም የመጥራራት ጣራው ነው»
( አልበሕሩል ሙሒጥ 8/39)

አንቀጿ ስለ አላህ አንድነት (ተውሒድ) እና ከሽርክና ሙሽሪኮች ስለ መጥራራት (በራአህ) የተያያዘች ስለሆነች እስከ ቂያማህ እለት ጥቅል መልእክት ይዛ ቀጣይ ነች።

ኢብኑ ተይሚያህ አንቀጿ የወረደችበትን ምክንያት ካብራሩ በኃላ  እንዲህ ይላሉ፦ «መልእክቱ ለአጠቃላይ ሙሽሪኮች ነው ላለፉትም እስከ ቂያማህ ድረስ ለሚመጡትም። በርግጥም (አላህ መልእክተኛውን ) ከርሱ ውጭ ካሉ ተመላኪዎች እንዲጥራሩ አዘዛቸው።ይህም የኢብራሂም ጎዳና ነው።እርሳቸውም በርሱ ጎዳና ላይ ተልከዋል።

አላሁ  ተዓላ እንዲህ አለ «ኢብራሂምም ለአባቱና ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡ እኔ ከምትግገዙት ሁሉ ንጹሕ ነኝ፡፡ከዚያ ከፈጠረኝ በስተቀር (አልግገዛም)፡፡ እርሱ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡በዝርዮቹም ውስጥ ይመለሱ ዘንድ (ባንድ አምላክ ማመንን) ቀሪ ቃል አደረጋት»

ይህች አንቀፅ ለካ  ሃዲያን እምነት እውቅና መስጠትን ታመላክታለች ያሉ ሰዎችን ኢብኑ ተይሚያህ ሙልሒድ ፣ ከሰዎች ሁሉ ውሸታምና ከሰዎች ሁሉ የባሱ ካ  ሀዲዎች ሲል ይቆጥራቸዋል።

እንዲህ ይላል፦ «ከመላሒዳዎች ይህ አንቀፅ የካ  ፊሮ ችን እምነት መውደድ ነው ብሎ ያሰበ እርሱ ከሰዎች ሁሉ የባሰ ውሸታምና የባሰ ካ ሀዲ ነው» (አልፉርቃን በይነ አውሊያኢረህማን ወአውሊያኢሸይጣን  1/79)

በድጋሜም  እንዲህ ይላል ፦ «ይህች ቃል የምታስፈርደው (መልእክተኛው)  ከእምነታቸው መጥራራታቸውን እንጂ መውደዳቸውን አይደለም»

(አልፉርቃን በይነ አውሊያኢረህማን ወአውሊያኢሸይጣን  1/79)

በድጋሜም  እንዲህ ይላሉ፦ «ይህች አንቀፅ ከሽርክ መጥራሪያ ነች። በርሷ ውስጥ የሙሽሪኮችንም ሆነ የየሁዳና ክርሰቲያኖችን እምነት መውደድ የለባትም፥ መላሒዳዎች እንደሚያስቡት።
እንዲሁም አንዳንድ ስህተተኞች እንደሚያስቡት በርሷ ውስጥ እነርሱን ከመ  ጋደል ክልከላ የለባትም ።የአላህ መልእክተኛ ለቅፅበት ያህል እንኳ የሙሽሪኮችን የየሁዳና ክርስቲያኖችን ሃይማኖትን ወድደው አያውቁም። አይ እርሳቸው ወድደው ያውቃሉ ብሎ የሚሞግትና በ “በላቸው «እናንተ ከሓ ዲዎች ሆይ! ያንን የምትግገዙትን (ጣዖት አሁን) አልግገዛም፡፡ እናንተም እኔ የምግገዛውን (አምላክም አሁን) ተገዢዎች አይደላችሁም፤እኔም ያንን የተገዛችሁትን (ወደፊት) ተገዢ አይደለሁም፣እናንተም እኔ የምግገዛውን (ወደፊት) ተገዢዎች አይደላችሁም፤ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ”  ማስረጃ የሚያቀርብ” (እርሱ ሙልሒድ ነው) ። 
(አልጀዋቡ ሶሒሕ ሊመን በድደለ ዲነል መሲህ 3/59)

ኢብኑል ቀይም  እንዲህ ይላሉ፦
“ይህች አንቀፅ ለነርሱ እምነት ወይም እነርሱን በእምነታቸው ላይ እውቅና መስጠትን የምታስፈርድ ከመሆን አላህ ፍፁም ጥራት የተገባው ነው።ይልቁንም የአላህ መልእክተኛና  ባልደረቦቻቸው  በዚህ ላይ ብርቱና ቀዳሚዎች ከመሆን አልተወገዱም ነበር። የእነርሱን እምነት በማውገዝ፣ በማነ ወርና በማጥ  ላላት ብርቱ ነበሩ።በሁሉም ጊዜና መድረክ ከልክለዋል፣ዝ ተ  ዋል፣ አስፈ  ራር ተዋል።

እነርሱም አማልክቶቻቸውን ከማውሳትና ከማነ ወር ከታቀቡ ምንም እንደማያደርጓቸው ነግረዋቸው ነበር።ሆኖም ግን (መልእክተኛው) የነርሱን ሃይማኖት ማውገዝና ማነ  ወርን እንጂ እምቢ አሉ፤ ታድያ እንዴት አንቀጿ ለነርሱ እውቅና መስጠትን ታስፈርዳለች ይባላል? ከዚህ ከንቱ ሙግት አላህ የጠራ ነው! አንቀጿ የምታስፈርደው እንዳሳለፍነው ጥርት ያለን መጥራራትን (በራአህ) ነው።

እነርሱ ያሉበትን ሃይማኖት በፍፁም አንስማማበትም፤ እርሱ ከንቱ ሃይማኖት ነው፤ እርሱ የነርሱ ብቻ ነው አንጋራቸውም ፣እነርሱንም በኛ እውነተኛ ሃይማኖት አናጋራቸውም። ይህ የመጥራራት ጣራው ነው።አንቀጿ በምን አግባብ እውቅና መስጠትን ይዛ ነው ስለ መሻርና ስለ “ልዩ” ነቷ (ተኽሲስ) የሚሞገተው? በሰይፍ ሲገጠሙና በማስረጃ ሲገጠሙ ትክክል እንዳልሆነ ገባህ? “ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ»
« ተፍሲር ኢበኒል ቀይም 2/255»

ኢብኑል ቀይም እንዲህ ይላሉ፦ «ልክ አንዲሁ ይህች መጥራራት ብይኗ በመልእክተኛው  ተከታዮችና የርሳቸውን መንገድ ተቃርነው ከርሳቸው ሱና ውጭ በሚጣሩ መካከል የፀናች ነች። የመልእክተኛው  ምትኮች (አህሉሱንናዎች) ለቢድዐህ ሰዎች “ለእናንተ ሃይማኖታችሁ አልላችሁ፡፡ ለእኔም ሃይማኖቴ አለኝ” ሲሉ ቢድዐቸውን እያፀደቁ መሆኑን አያስይዝም።ይልቁንም ይህ እኛ ከርሷ መጥራራታችን ነው እያሉ ነው ። ከዚህም ጎን ለጎን እነርሱ ላይ ምላሽ በመስጠትና በመታገል ይቆማሉ።»
(ተፍሲር ኢብኒል ቀይም 2/256)

ለመጀመሪያ ጊዜ ይህችን  አንቀፅ ለኩ  ፋ ሮች የሃይማኖት ነፃነት ማስረጃ  ያደረገው ሰው ፦

Ismaiil Nuru

04 Oct, 23:04


የጅማ ኢማም የሺርክ አናቅፅቶችን በማጣቀስ
መውሊድን ሲያወግዝ በዚሁ አንደበት ግልፁን ሺርክ ኢሬቻን ማውገዝ አልቻለም።

የሳኡዲ ኢማም የመውሊድን ቢድዐነት ባስጠነቀቀበት ሚንበር ከመውሊድ በሳምንት ልዩነት አፍንጫው ስር የተከበረውን የዒደል ወጠኒ ቢድዐነት መተንፈስ አልቻለም።

የኢሬቻ ቀለማት ትርጉም ሺርክነትን የሚያስረዳው የወሎ ብሄርተኛ «አልሐምዱሊላህ ታቦታችን በሰላም ገባ»ን  የተፈለገበት ሌላ ትርጉም ነው ብሎ ከማስቀየስ ውጭ  ማውገዝ አልቻለም።

ሌላውም እንዲሁ እንዲሁ ....


ዓሊምና ዳዒ ለአካባቢው መንግስት ወይም ሰፊ ህዝብ ፍላጎት ካደረ እርሱ የዲን ኻዲም ሳይሆን ካድሬ ነው። የዳዕዋ አልጎሪዝም እንዲህ በሆንማ  አንድም ነብይ ጠላት ተደርጎ አይያዝም ነበር ! 

የቴሌግራም ቻናል፦ t.me/ismaiilnuru

Ismaiil Nuru

03 Oct, 11:45


የብሄር ፖለቲካው የፈጠረው የዳዕዋ «ስታይል»

ዱዐቶች -አውቀው ላይሆን ይችላል- እዚህ ስነልቦና ውስጥ ግን ገብተዋል። ስለ አንድ ጉዳይ ለማስጠንቀቅ እገሌን ይከፋዋል /እገሌም እንዳይከፋው አይነት አካሄድን ሲመርጡ አያለሁ።

የዚህ ማሳያ የመስቀልና የኢሬቻ በአላት ላይ የሚደረጉ ዳዕዋዎች ናቸው።«ኢሬቻን ማክበር ሀራም ነው መስቀልን (ደመራ) ማክበር ሀራም እንደሆነው ሁሉ» አይነት ይዘት ያለው የደዕዋ አካሄድን እየተከተሉ ነው።

ኢሬቻን የሚያከብረው የኦሮሞ ብሄርተኛ የኔ ብቻ ተነካ ብሎ እንዳይቆጣ «ያንተን ብቻ ሳይሆን ደመራንም አውግዣለሁ» አይነት አንደምታ አለው። በሌላኛው ሳይድ ደግሞ የአማራው ብሄርተኛ እንዳይከፈው መስቀልን ብቻ ሳይሆን ኢሬቻንም አውግዥለሁ አይነት አካሄድ አለበት።     

አንድን መጥፎ ነገር የምናወግዘው አላህ ባስጠነቀቀበት መጠን እንጅ በእነ እገሌ የስሜት ዝንባሌ ልኬት አይደለም።

አማራነት አንድ ያደርገናልና  መስቀልን አብሬው  ካላከበርኩ የሚለውና የደመራ እንጨት የሚያቀርበው በአማራ ብሄርተኝነት የታወረው የአማራ «ሙስሊም» የሚፈፅመውም የኩ  ፍር ተግባርም ይሁን ኦሮሞነት አንድ ያደርገናል በማለት ለጣጙት የሚሰግድ የኦሮሞ «ሙስሊም» የሚፈፅሙት ክህደትና ሺርክ ነው።

ነገር ግን ጉዳዮቹ የሚታዩበት (ባብ) የተለያየ ሊሆን ይችላል። መስቀልን ካላከበርኩ የሚለው ደዩስ ብይን የሚሰጥበት «በካሀዲያን መመሳሰል» በሚል ርእስ ስር ነው። ኢሬቻን የሚያከብረው ሌላኛው ደዩስ ደግሞ ጉዳዩ የሚታይለት «ሽርክን የፈፀመ» በሚለው ርእስ ስር ነው።  ሁለቱም ክህደት መሆናቸው ግን ሁሌም ይሰመርበታል።

ያም እንዳይከፋው ይሄም እንዳይከፋው ሲባል የሚኬድ አካሄድ ግን አይሰራም። ለምሳሌ ዋቄፈና ያረደውን መብላት አይፈቀድም።ክርስቲያን ያረደውን (ኪታቢይ ስለሆኑ) መመገብ ግን ይፈቀዳል። ዋቄፈናው እንዳይከፋው ተብሎ ሙሽሪክ ያረደውን መብላት ይፈቀዳል ሊባል ነው ?

ትክክለኛው አካሄድ መውሊድ ሲደርስ ስለ መውሊድ ቢድዐነት ፣ መስቀል ወይም ሌላ የክርስቲያኖች በአል ሲደርስ በእምነት መገለጫዎች መመሳሰል ኩ ፍ  ርነት ፣ ዒደል ወጠኒ ሲደርስ ስለ ቢድዐነቱ ፣  ኢሬቻ ሲደርስ ደግሞ ስለሺርክነቱ ማስተማር ነው።

ብሄርተኛ ሙስሊሞች ከተቀየሙስ? 

መስቀል ተነካብኝ የሚል «ሙስሊም» ካለ  በደመራ ጭስ ታ ፍኖ መ ሞት ይችላል። ኢሬቻ ተነካብኝ የሚል «ሙስሊም» ካለም የባህር ውሃ ተግቶ መ ሞት ይችላል።

አላህ እንዳለው ፦

«لِّيَهْلِكَ مَنْ هَلَكَ عَن بَيِّنَةٍ وَيَحْيَىٰ مَنْ حَيَّ عَن بَيِّنَةٍ ۗ وَإِنَّ اللَّهَ لَسَمِيعٌ عَلِيمٌ»
(አል አንፋል 42)

የቴሌግራም ቻናል ፦ t.me/ismaiilnuru

2,070

subscribers

178

photos

10

videos