AAU - Muslim Students Union @aaumsu Channel on Telegram

AAU - Muslim Students Union

@aaumsu


This is the official channel of AAU-MSU.

Email: [email protected]
Telegram: @aaumsu
Group: @aaumsu_discussion
Twitter: twitter.com/aaumsu12
Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303

Contact us: @Aaumuslimstudentsunion1

AAU - Muslim Students Union (English)

Are you a Muslim student looking to connect with like-minded individuals and engage in meaningful discussions? Look no further than AAU - Muslim Students Union! This channel serves as the official platform for AAU-MSU, where students from all backgrounds come together to share ideas, resources, and support.

By joining AAU-MSU, you gain access to a vibrant community that is dedicated to promoting unity, diversity, and understanding among Muslim students. Whether you're looking for study groups, networking opportunities, or simply a space to share your thoughts, AAU-MSU has you covered.

Want to stay updated on the latest events and initiatives from AAU-MSU? Make sure to follow us on our various social media platforms:

Email: [email protected]
Telegram: @aaumsu
Group: @aaumsu_discussion
Twitter: twitter.com/aaumsu12
Facebook: facebook.com/profile.php?id=100087931837303

Join AAU - Muslim Students Union today and be a part of a supportive community that values your voice and contributions. We look forward to connecting with you!

AAU - Muslim Students Union

22 Feb, 15:21


የተመዘገባችሁ ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ! ስለ ንቁ ምላሻቹ እያመሰገንን በቂ ሰዎች ስለተገኙ ከዚህ በኃላ ተጨማሪ ተመዝጋቢ አንቀበልም

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Feb, 14:09


Male Volunteers needed!

በነገው ዕለት ለሚካሄደው የነሲሓ ኮንፈረንስ አስተባባሪ ስለሚያስፈልግ ፍላጎቱ ያላችሁ ወንድሞች በ @Aaumuslimstudentsunion1 አናግሩን።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Feb, 14:07


የንፅፅር ትምህርት ለምትከታተሉ ወንድም እና እህቶች፡

በነገው ዕለት የነበረው ፕሮግራማችን በሱና ዩኒቨርሲቲ የምርቃት ፕሮግራም እና ነሲሓ ኮንፈረንስ ምክንያት አብዛኛው ተማሪዎች አስተባባሪ እና ተሳታፊ በመሆናቸው የነገው ፕሮግራም አይኖርም። ኢንሻላህ በቀጣይ ሳምንት ቅዳሜ የምንቀጥል ይሆናል።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Feb, 11:38


ኒቃብ ከመማር ከመሸለም ከመምራት እንደማያግድ ያሳዩት የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተሸላሚዎቹ ዛኪራ ተባረክ እና ራህማ አንሷር ከሁሉም የህክምና ተማሪዎች አንደኛ እና ሶስተኛ እንዲሁም ከሴቶች አንደኛ እና ሁለተኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆነዋል!!!

ኒቃብ የመማር ማስተማር ሂደቱን ይጎዳል ብለው ለመከልከል ለሚጋጋጡት ላኩላቸው

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

21 Feb, 01:50


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

19 Feb, 18:46


...السَّلَامُ عَلَيْنَا وَعَلَى عِبَادِ اللَّهِ الصَّالِحِينَ...
...ሰላም በኛ ላይ ይሁን፤ በአላህ ሷሊሕ ባሮችም ላይ...

ይህን ዱዓ ከዛሬ 1400 ዓመታት አካባቢ ጀምሮ ያሉ ሰጋጆች ሁሉ በቀን አምስት ጊዜ ደጋግመውታል። እስከ ዕለተ ቂያማ ያሉ ሙዕሚኖችም እንዲሁ ይደጋግሙታል። የነዚህ ሁሉ ዱዓ እንዲደርሰው የፈለገ ከሷሊሖች ይሁን!

ሷሊሕ ማለት የአላህን እና የፍጡራኑን ሐቅ የሚወጣ ማለት ነው።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

18 Feb, 19:02


من أعظم الأدب عدم تعلق العبد بالمخلوقين في أمور الدنيا، ولو كان يسيرًا

ከታላላቅ የስነ-ምግባር ዓይነቶች አንዱ፤ ባሪያው በዱንያ ጉዳይ ምንም ኢምንት ቢሆን እንኳን ከፍጡራን ምንም አለመፈለግ ነው።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

18 Feb, 03:32


"በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ፤ ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡
" (አን-ናዚዓት 40 - 41)

የኢማንህን ሁኔታ ማወቅ ከፈለግክ ብቻህን ስትሆን እራስህን ተመልከት። ቀደምት ሷሊሖች ነፍሳቸውንና ፍላጎቷን የሚታገሉ ነብሩና።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

17 Feb, 12:32


የተመዘገባችሁ ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ! ስለ ንቁ ምላሻቹ እያመሰገንን በቂ ሰዎች ስለተገኙ ከዚህ በኃላ ተጨማሪ ተመዝጋቢ አንቀበልም

©AAU6KiloJemea

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

17 Feb, 10:40


የአአዩ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች የዳዕዋ እና ትምህርት ማህበር (ኢሙዳት) ጋር በመተባበር ላዘጋጁት የአጭር ጊዜ የንጽጽር ትምህርት ምዝገባ ዛሬ ማታ ይጠናቀቃል!

ለመመዝገብ፡ https://forms.gle/qEiPWSPfH3PzVP2m6

ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት በ @Aaumuslimstudentsunion1 ያናግሩን።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

17 Feb, 07:21


Volunteers needed!!

ቀጣይ እሁድ(የካቲት 16) ኤልያና ሆቴል በሚካሄደው የሱና ዩኒቨርስቲ የመሻይኾቸ ምርቃት ላይ ከጀማአችን 10 በጎ ፈቃደኛ ወንድ አስተባባሪዎች ይፈለጋሉ። እሁድ የካቲት 16 ኤልያና ሆቴል በመገኘት ማገዝ የምትችሉ ወንድሞች በ @skmsj_fb_bot አሳውቁን።

©️AAU6KiloJemea

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Feb, 10:47


"መጨረሻይቱንም ዓለም የፈለገ ሰው እርሱ አማኝ ኾኖ ለርሷ (ተገቢ) ሥራዋን የሠራም ሰው እነዚህ ሥራቸው የተመሰገነ ይኾናል፡፡" (አል-ኢስራእ 19)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Feb, 09:02


የአጭር ጊዜ የንፅፅር ስልጠና ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከኢትዮጵያ ሙስሊሞች የዳዕዋ እና ትምህርት ማህበር ጋር በመተባበር ልዩ የአጭር ጊዜ የንፅፅር ስልጠና እንዳዘጋጀ ሲገልፅ ከታላቅ ደስታ ጋር ነው:: ትምህርቱ የፊታችን ቅዳሜ የካቲት 15 የሚጀምር ሲሆን ለአራት ሳምንታት የሚቆይ ሲሆን የንፅፅር፣ atheism እና ሹብሃት የመሳሰሉ ወሳኝ እና ቁልፍ የሆኑ የትምህርት ዘርፎችን አካቶ ይዟል።

አጠቃላይ ትምህርቱ በአል-አቅሷ መስጂድ በየሳምንቱ ቅዳሜ እና እሁድ ከጠዋቱ 03፡00 - 06፡00 የሚሰጥ ሲሆን ትምህርቱን በተገቢው ሁኔታ ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ከAAU ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት እና ከኢሙዳት የጋራ የምስክር ወረቀት የሚያገኙ ይሆናል።

ለመመዝገብ፡ https://forms.gle/qEiPWSPfH3PzVP2m6

ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት በ @Aaumuslimstudentsunion1 ያናግሩን።

የዚህ ልዩ እድል ተቋዳሽ በመሆን እወቅትዎን ያሰፉ ዘንድ ጋበዝንዎ። ለሚወዱት ሁሉም በማጋራት ውዴታዎን ይግለፁ።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

14 Feb, 12:23


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የሰላም ሚኒስትር በዩኒቨርሲቲው አዲሱ የተማሪዎች የስነ ምግባር መመሪያ ውስጥ ያሉ አድሎኣዊ ድንጋጌዎችን እና አሰራሮችን እንዲመረምር ጠየቀ!

ህብረቱን ጥያቄውን ያቀረበው ለሚኒስትር መስሪያ ቤቱ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ከኒቃብ እና የጀመዓ ሰላት ጋር ተያይዞ እየደረሱ ስላሉ የመብት ጥሰቶች ለማብራራት በጻፈው ደብዳቤ ነው። ህብረቱ ችግሩ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ለወራት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቢጥርም በዩኒቨርሲቲው በኩል ችግሩን የመፍታት ፍላጎት ባለመኖሩ እንዳልተሳካም አውስቷል።

ህብረቱ እና ሙስሊም ተማሪዎች ለሰላምና ሰላማዊ ትግል ካላቸው ጽኑ አቋም የተነሳም በአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ሙሉ ወጪ የጣት አሻራ መመርመሪያ ማሽኖችን ለዩኒቨርሲቲው ለማስገባት ዝግጁ ቢሆኑም ነገር ግን የዩኒቨሪሲቲው አስተዳደር ችግሩን ከመፍታት ይልቅ ችላ በማለት እንዲባባስ እያደረገ ይገኛል ሲል ደብዳቤው አብራርቷል።

አሁንም ድረስ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ኒቃብ በሚለብሱ እህቶች ላይ በተለይም ግቢ መግቢያ በሮች ላይ ትንኮሳዎች እየተካሄዱ በመሆኑ ጉዳዩ በአስቸኳይ እልባት የማያገኝ ከሆነ ወዳልተፈለገ ደረጃ ሊያመራ እንደሚችልና ወደዚያ ቢያመራም ብቸኛ ተጠያቂ ዩኒቨርሲቲው እንደሚሆን አሳስቧል።

በመሆኑም የሰላም ሚኒስትር የሐገሪቱን ሰላምና መረጋጋት እንዲያስጠብቅ ኃላፊነት የተሰጠው ተቋም በመሆኑ ችግሩን ለመፍታት አስቸኳይ እና ቆራጥ እርምጃ እንዲወስድ ጠይቋል።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

14 Feb, 03:23


አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ👋👋

የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት አካዳሚክ ሴክተር ለሴት ፍሬሽ ተማሪዎች ልዩ የሆነ ኘሮግራም ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል።
📄በፋይናል ፈተናችሁ ጥሩ ውጤት እንድታመጡ እየተመኘን ቀጣይ እርምጃችሁ የሚሆነው የዲፓርትመንት መረጣ በመሆኑ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ስለሚሰጡ ዲፓርትመንቶች ለሁሉም ካምፓስ ፍሬሾች በቂ የሆነ መረጃ ለማቅረብ ዝግጅታችንን አጠናቀናል። በምትመርጧቸው ዲፓርትመንቶች ላይ እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች ተሳትፈው, ስላለው የትምህረት አሰጣጥ እና ሁኔታ ገለፃ የሚያደሪርጉላችሁ ይሆናል።

📍 ቦታ: አቅሳ መስጂድ
🕰 ሰዐት: ጠዋት 2:45 - 6:00
📅 ቀን: ቅዳሜ, Feb 15 (የካቲት 8)

ሁላችሁም ተጋብዛቿል 😊
ከታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ
👉Link

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

14 Feb, 00:35


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

13 Feb, 14:59


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በዩኒቨርሲቲው ያሉ ሙስሊም ተማሪዎችን መብት እና ክብር ለማስጠበቅ ቆራጥ እና አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስድ ጠየቀ!

ህብረቱ ለምክር ቤቱ በጻፈው ደብዳቤ በዘንድሮው አመት በዩኒቨርሲቲው አዲስ ከጸደቀው የተማሪዎች ስነምግባርና ዲሲፕሊን መመሪያ ጋር በተያያዘ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ከኒቃብ እና የጀመዓ ሰላት ጋር ተያይዞ እየደረሰ ስላለው ችግር በሰፊው አብራርቷል። ህብረቱ ችግሩ ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ለወራት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቢጥርም በዩኒቨርሲቲው በኩል ችግሩን የመፍታት ፍላጎት ባለመኖሩ እንዳልተሳካም አውስቷል።

ይህም በእንዲህ እንዳለ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተለይም ኒቃብ በሚለብሱ እህቶች ላይ በተለይም ግቢ መግቢያ በሮች ላይ አሁንም ድረስ ትንኮሳዎች እየተካሄዱ እንዳሉ በመጥቀስ ጉዳዩ በአስቸኳይ እልባት የማያገኝ ከሆነ ወዳልተፈለገ ደረጃ ሊያመራ እንደሚችል ተብራርቷል።

በተጨማሪም ህብረቱ ፕሬዝደንቱና ስራ አስፈጻሚውን ጨምሮ ምክር ቤቱን በተደጋጋሚ በጉዳዩ ዙሪያ ለማነጋገር ቢሞክርም ከምክር ቤቱ ምላሽ አለማግኘቱ እና በዚህ ወቅት ምክር ቤቱ ከተማሪዎች ጎን አለመቆሙ ኃላፊነቱን አለመወጣት ብቻ ሳይሆን ሙስሊሙ ማህብረሰብ በምክር ቤቱ ላይ የጣለውን አደራ መክዳት እና የታሪክ ተወቃሽ መሆንም ጭምር በመሆኑ ምክር ቤቱ በአፋጣኝ መፍትሄ ያበጅ ዘንድ ጠይቋል።

ህብረቱ የደብዳቤውን ግልባጭ ለዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ጽ/ቤት፣ ለአዲስ አበባ እ/ጉ/ከ/ም/ቤት፣ ለኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት አስገብቷል።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

12 Feb, 15:29


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የጁምዓ ሰላት ሰዓት እንዲከበር አሳሰበ።

ህብረቱ ለዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት እና በግልባጭ ለአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ባስገባው ደብዳቤ የሐገራችን መንግስት ሙስሊም ሰራተኞች የጁምአ ሰላትን እንዲሳተፉ ለማድረግ የመንግስት መስሪያ ቤቶች አርብ ከ 05፡30 እስከ 07፡30 እንዲዘጉ መመሪያ ያወጣና የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንትን ጨምሮ የዩንቨርስቲው አመራሮች ለመመሪያው መተግበር ቁርጠኛ መሆናቸው የገለጹ ቢሆንም ባለፉት ጊዜያት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በውጤታማነት አለመተግበሩን ጠቅሷል።

ህብረቱ የትምህርት ዘመኑ ሁለተኛ ሴሚስተር እየተጀመረ በመሆኑ የተማሪዎች ህብረት እና ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉም የአካዳሚክ መርሃ ግብሮች የጁሙዓ የሰላት ጊዜን በሚመለከት የመንግስት እና የዩኒቨርሲቲ መመሪያዎችን መተግበራቸው እንዲከታተሉና ስህተቶችን እንዲያርሙ አጥብቀን አሳስቧል።

ህብረት በየካምፓስ ተወካዮቹ አማካኝነት ሁኔታውን በቅርበት የሚከታተል እና የሚፈጸሙ ጥሰቶችን የሚያሳውቅ መሆኑንና ከዚህ መመሪያ ውጭ የሆነ ማንኛውም አካል ተጠያቂ የሚሆንበትም መንገድ እንዲመቻች ጠይቋል።

የህብረቱ ተወካዮች ከተማሪዎች ህብረት ጋር በጉዳዩ ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን የተማሪዎች ህብረትም ጥያቄው ተገቢ መሆኑን በመጥቀስ አፈጻጸሙን እንድሚከታተል ገልጿል። የአአዩሙተህ በካምፓስ ጀመዓዎቹ አማካኝነት አተገባበሩን የሚከታተል ሲሆን የዩኒቨርሲቲያችን ሙስሊም ተማሪዎች በየትምህርት ክፍሎቻቸው እንዲከታተሉ እና ለህብረቱ እንዲያሳውቁ እናሳስባለን።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

12 Feb, 15:01


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ተወካዮች በዩኒቨርሲቲው የረመዳን ዝግጅት ዙሪያ ከዩኒቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ጋር ተወያየ።

በውይይቱም ወቅት የህብረቱ ተወካዮች መደረግ ስላለባቸው ዝግጅቶችና ከዚህ በፊት ስለነበሩ ችግሮች ማብራሪያ ሰጥተዋል። ተወካዮቹ የካፌ እና ለተራዊህና ተሃጁድ ሰላቶች የበር መውጫና መግቢያ ሰዓቶች ልክ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ እንዲስተካከሉ አስታውሰዋል።

በተጨማሪም የመጀመሪያ ቀን የሱህር ምግብ አለመዘጋጀት ወይም በቂ ያለመሆንን ባለፉት አመታት ሲታይ የነበረ ችግር በመሆኑ እንዲፈታ ያሳሰቡ ሲሆንም የተማሪዎች ህብረትም ዘንድሮ ችግሩ ሙሉ በሙሉ እንዲቀረፍ እንደሚሰራ አሳውቋል።

ሌላው ከምግብ ጥራት ጋር በተያያዘ በተለይ በሱህር ሰዓት የሚዘጋጁ ምግቦች በአብዛኛው ጥራታቸውን ያልጠበቁ መሆናቸውን የተገለጸ ሲሆን የተማሪዎች ህብረት በየጊዜው ቁጥጥር እንዲያደርግ ስምምነት ተደርሷል። ከዚያም በተጨማሪ ከተማሪዎች ህብረት ከሚመደቡ ተቆጣጣሪዎች በተጨማሪ በየካምፓሱ ከሙስሊም ተማሪዎች አንድ አንድ ተቆጣጣሪ እንዲመደብ ከስምምነት ተደርሷል።

ሌላው በውይይቱ የተነሳው ነጥብ የሸዋልን ስድስት ቀናት ለሚጾሙ ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው አገልግሎት እንዲሰጥ የሚል ሲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ውይይት እንዲደረግ በመስማማት ውይይቱ ተጠናቋል።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

12 Feb, 03:42


"የፈጅርን ሰላት በጀመዓ መስገድ ለእኔ ለሊቱን በሶላት ከማሳለፍ የበለጠ ውድ ነው።"

- ዑመር ኢብን አል-ኸጧብ

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

11 Feb, 03:34


"ፍጹም ምእምናን እነዚያ አላህ በተወሳ ጊዜ ልቦቻቸው የሚፈሩት፣ በነሱም ላይ አንቀጾቻችን በተነበቡ ጊዜ እምነትን የሚጨምሩላቸው፣ በጌታቸውም ላይ ብቻ የሚመኩት ናቸው፡፡ እነዚያ ሶላትን ደንቡን አሟልተው የሚሰግዱ ከሰጠናቸውም ሲሳይ የሚለግሱ ናቸው፡፡ እነዚያ በእውነት አማኞች እነሱ ብቻ ናቸው፡፡ ለእነሱ በጌታቸው ዘንድ ደረጃዎች ምህረትና የከበረ ሲሳይም አላቸው፡፡" (አል-አንፋል 2-4)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Feb, 06:58


"የሙስሊሞች ጉዳይ ያላሳሰበው ከኛ አይደለም"

- ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

07 Feb, 06:13


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

06 Feb, 16:14


የExit Exam ሰዓት ለውጥ እንደተደረገ ትምህርት ሚኒስቴር በይፋ አሳውቋል::

ፍትሐዊ እና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

06 Feb, 09:22


"አርብ እለት በሚሰጠው ፈተና ላይ የጁሙአ ሰላትን ምክንያት በማድረግ በትምህርት ሚኒስቴር የሰአት ማሻሻያ ተደርጓል።"

- ሰመራ ዩኒቨርሲቲ

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

06 Feb, 07:13


የExit Exam የመፈተኛ ሰዓት ለጁምዓ እንደተቀየረ ድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ: ደብረ ብርሐን ዩኒቨርሲቲ እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ አሳውቀዋል::

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

05 Feb, 18:30


ጁምዓ እና የመውጫ ፈተና (Exit Exam) UPDATE!

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

የትምህርት ሚኒስቴር በጁምዓ ቀን የተማሪዎችን መብት በመጣስ ከ5:30 - 8:00 የመውጫ ፈተና ለመስጠት ማሰቡን ተከትሎ ህብረታችን ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቅሬታ ደብዳቤ  ማስገባቱ ይታወቃል:: ይህንንም ተከትሎ የህብረቱ ተወካዮች በዛሬው እለት ከትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር ዴኤታ ፅ/ቤት በተሰጣቸው መልስ በፕሮግራሙ ላይ ማስተካከያ እንዳደረጠ አሳውቋል::  በዚህም መሠረት በመጪው ጁምዓ የሚሰጠው Exit Exam ከ7:30-10:00 እንደሚሆን ገልፇል:: ይህንንም ለሚመለከታቸው አካላት እንዳሳወቁ ገልፀዋል:: ሆኖም ግን እስካሁኑ ሰዓት ድረስ በይፋ ማስታዎቂያ ያሳወቀው ነገር የለም:: እኛም የሚኖሩ ሁነቶችን እየተከታተልን ለማስተካከል የምንሰራ መሆናችንን እንገልፃለን::

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

04 Feb, 17:58


የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን (Exit Exam) በመጪው አርብ በጁምዓ ሰዓት ማለትም ከ5:30-8:00 ለመስጠት ያወጣውን ፕሮግራም እንዲቀይር ጠየቀ!

•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ጥር 27 / 2017 ዓ.ል
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ህብረቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ባስገባው ደብዳቤ ጁምዓ የሙስሊሞች ሳምንታዊ በዓል መሆኑንና ከ5:30-7:30 በሀገር ደረጃ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እረፍት መሆናቸውን ጠቅሶ በዚህ ሰዓት የፈተና ፕሮግራም ማውጣት የሙስሊም ተማሪዎችን እሴቶችን እና መብቶችን መጋፋት እንደሆነ ገልፇል:: መሠል ጥፋቶች መደጋገማቸው ሙስሊሙን ተማሪ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያራርቁ በመሆናቸውም ተመሳሳይ ችግሮች በዘላቂነት እንዳይፈጠሩ መስመር እንዲደረገም ጠይቋል::

የደብዳቤው ግልባጭ ለፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ገብቷል::

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

03 Feb, 06:20


የትምህርት ሚኒስቴር Exit Examን በጁምዓ ሰዓት አድርጓል!

ጁምዓ ቀን በመንግስት መስሪያ ቤቶች ደረጃ ከ5:30 - 7:30 ለስግደት በሚል ዝግ እንደሆነ ይታወቃል:: የፌደራል መጅሊስ በቅርቡ በሰጠው ፈታዋም የጁምዓ ሶላት የደረሰበት ማንኛውም ሙስሊም ወደ መስጂድ ሄዶ መስገድ ግዴታው እንደሆነ አሳውቋል:: ሆኖም የትምህርት ሚኒስቴር የመውጪያ ፈተናን በመጪው ጁምዓ ከ5:30 - 8:00 ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቶ ሙስሊም ተማሪዎችን ከጁምዓ ሶላትና ከፈተናቸው እንዲመርጡ የሚያስገድድ ሁኔታ ፈጥሯል:: ይህ ሀገራችንን የምትመራበትን መመሪያ መጣስ ብሎም የሙስሊም ተማሪዎችን መብት መዳፈር ነው::

በትምህርትም ሆነ በፈተና ፕሮግራም ከትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ ከዩኒቨርሲቲዎች ወይንም ከበታች ትምህርት ቤቶች በተደጋጋሚ የሚፈፀሙ የመብት ጥሰቶች በዘላቂነት ሊፈቱ ይገባል:: ካላንደር ከሌላቸው ወይንም ስለሙስሊሙ መሠረታዊ መብቶች እውቀቱ ከሌላቸው እንዲያውቁ ይደረጉ:: እየረሱ ወይንም ሆን ብለው እያበላሹ ከሆነ ደግሞ መንግስት ብዙም የማይረሳና የማያበላሽ ሰው በቦታው ላይ ያስቀምጥ::

©️EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

02 Feb, 16:12


በነገው ዕለት final exam የምትጀምሩ የመጀመሪያ አመት ወንድምና እህቶች ሁሉ መልካም እድል እንመኛለን።

አላህ ፈተናችሁን ያገራላችሁ ዘንድ ዱዓችን ነው፤ ካሰባችሁት በላይ ያቅልልላችሁ፤ ጥሩን ውጤት ይወፍቃችሁ፤ በሰላም ጀምራችሁ በሰላም የምትጨርሱ ያድርጋችሁ። ከፈተናውም በኃላ ለራሳችሁም፣ ለሙስሊሙም ማህበረሰብ የምትጠቅሙበትን የትምህርት ክፍል ይወፍቃችሁ።

ፈተናውን ጀምራችሁ እስከምትጨርሱ ኢስላማዊ አደብ እና ስነ-ምግባር ትላበሱ ዘንድ እና ለጊዜያዊ ጥቅምና ደስታ ብላችሁ ጌታችሁን የሚያስቆጣ ድርጊት ከመፈጸም ትቆጠቡ ዘንድ አደራችን ነው!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

31 Jan, 07:43


የተዘገባችሁ ሁሉ ጀዛኩሙሏሁ ኸይራ! በቂ ሰዎች ስለተገኙ ከዚህ በኃላ ተጨማሪ ተመዝጋቢ አንቀበልም።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

31 Jan, 00:33


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

30 Jan, 14:48


"አላህንም በደለኞች ከሚሠሩት ግፍ ዘንጊ አድርገህ አታስብ፡፡ የሚያቆያቸው ዓይኖች በእርሱ እስከሚፈጡበት ቀን ድረስ ብቻ ነው፡፡" (ኢብራሂም 42)

ቁርኣንን በአደባባይ በማቃጠል የሚታወቀው ኢራቃዊው ክርስቲያን ሰልዋን ሞሚካ በስዊድን በቲክቶክ የቀጥታ ስርጭት ላይ እያለ በተተኮሰበት ጥይት ተገድሏል። ይህ ሰው በኢራቅ ውስጥ የሚንቀሳቀስ የክርስቲያን ሚሊሻ ቡድን መሪ ነበር። በሰራቸው አስከፊ ወንጀሎች ሳቢያ በህግ ሲፈለግ አምልጦ ስዊድን የገባ ሲሆን ጥገኝነት ጠይቆ ነበር።

ይህ ሰው ቁርዓንን በተደጋጋሚ ሲያቃጥል ሙስሊሞች ቢቃወሙም "ነጻነት" በሚል ካባ ከለላ ሲደረግለት ነበር። ፍትሕ በመደበኛው በር በተደጋጋሚ ሲንኳኳ ምላሽ ካልተገኘ፤ ሰዎች በጓሮ በር ሂደው መብታቸውን ማስከበራቸው ተፈጥሯዊ ነው። ሰውዬውም የሚገባውን አግኝቷል።

ይህ አጋጣሚ በኛም ሐገር ያላቸውን ስልጣን ተማምነው ሙስሊሞችን ለሚበድሉ ሁሉ መልዕክት ይሆናል፤ የተገፋ ህዝብ ሁልጊዜ መብቱን አይለምንም፣ የሆነ ጊዜ በራሱ መንገድ ያስከብረዋል እንጂ!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

30 Jan, 12:52


Volunteers needed!

እሁድ ጥር 25 በመዲናችን አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ስቴዲየም ለሚካሄደው 2ኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውድድር ስኬታማነት በጎ ፈቃደኛ አስተባባሪዎች ይፈለጋሉ። ከግቢያችንም ከወንዶች እና ሴቶች በአጠቃላይ 30 አስተባባሪዎች ስለሚፈለጉ እሁድ ከጠዋቱ 12፡30 ጀምሮ ቦታው በመገኘት ማገዝ የምትችሉ ወንድም እና እህቶች በ @Aaumuslimstudentsunion1 አሳውቁን።

ማሳሰቢያ፡ አስተባባሪዎች የሚፈለጉት በሁለቱም ጾታዎች ሲሆን ያለምንም ክፍያ ውድድሩን የመታደም እድል ያገኛሉ።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

30 Jan, 11:45


ማሊክ ኢብኑ አነስ የሚከተለው ታሪክ እንደተነገራቸው ጠቅሰዋል፦
"በአንድ ወቅት የአላህ መልዕክተኛ ድምጽ ከፍ ተደርጎ ከሚሰገድባቸው ሰላቶች አንዱን በሚያስገዱ ጊዜ አንድን አንቀጽ ዘለሉ። ሰላቱንም ከጨረሱ በኃላ ዞር ብለው፦ "እከሌ ሆይ፣ ከዚህ ሱራ የተውኩት (አንቀጽ) አለን?" ብለው ጠየቁ፤ እርሱም "አላውቅም" በማለት መለሰ። እንደዚሁ ሁለት ወይም ሶስት ሰዎችን ጠየቁ፤ ሁሉም "አናውቅም" በማለት መለሱ። ከዚያም የአላህ መልዕክተኛ "ኡበይ አለን?" ብለው ሲጠይቁ "አዎን አለ" የሚል ምላሽ አገኙ። መልዕክተኛውም "እንግዲያውስ ለዚህ ጉዳይ ብቁው እርሱ ነው" አሉና "ኡበይ ሆይ፣ ከዚህ ሱራ የጣልኩት አለን?" በማለት ጠየቁት። እርሱም "አዎ፣ እንዲህ እንዲህ የምትለዋን አንቀጽ" በማለት መለሰ። የአላህ መልዕክተኛም "እንዳታስተካክለኝ ምን ከለከለህ?" ብለው ሲጠይቁት "ተሽሮ ነው ብዬ አስቤ ነው" አለ። የአላህ መልዕክተኛም የሚከተለውን አሉ፦

"የአላህ መጽሐፍ እየተነበበላቸው ምን እንደሚነበብ የማያውቁ ሰዎች ችግራቸው ምንድነው? የአላህ ታላቅነት ከበኒ ኢስራኢሎች ልብ የተነሳው እንደዚሁ ነው። አካሎቻቸው (በመገኘት) ይመሰክራሉ፤ ልቦቻቸው ግን የሉም። አላህ ልቡም አካሉም ካልተሰበሰ በስተቀር አላህ የአንድን ባሪያ ስራ አይቀበልም።"

ጃሚዕ አል-ኡሱል፤ ኢብን አል-አሲር

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

30 Jan, 09:03


﴿وَجَعَلْنَا ٱلَّيْلَ وَٱلنَّهَارَ ءَايَتَيْنِ ۖ فَمَحَوْنَآ ءَايَةَ ٱلَّيْلِ وَجَعَلْنَآ ءَايَةَ ٱلنَّهَارِ مُبْصِرَةًۭ لِّتَبْتَغُوا۟ فَضْلًۭا مِّن رَّبِّكُمْ وَلِتَعْلَمُوا۟ عَدَدَ ٱلسِّنِينَ وَٱلْحِسَابَ ۚ وَكُلَّ شَىْءٍۢ فَصَّلْنَـٰهُ تَفْصِيلًۭا﴾

"ሌሊትንና ቀንንም (ለችሎታችን) ምልክቶች አደረግን፡፡ የሌሊትን ምልክትም አበስን፡፡ የቀንን ምልክትም የምታሳይ አደረግን፡፡ (ይህም የኾነበት) ከጌታችሁ ትርፍን ልትፈልጉ የዓመታትንም ቁጥርና ሒሳብንም ታውቁ ዘንድ ነው፡፡ ነገሩንም ሁሉ ለያይተን ዘረዘርነው፡፡" (አል-ኢስራእ 12)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Jan, 13:01


NOTE: ከሒጃብ ከኒቃብም ሆነ ከየትኛውም የሙስሊም ተማሪዎች መብት ጋር ተያይዞ "ተፈቀደ!" የሚልን ቃል አንጠቀም:: መብቶቻችን እንደ እስልምና ግዴታ የተደረጉ እና እንደ ሕገ-መንግስት ደግሞ እውቅና የተቸራቸው ናቸው:: ማንም አካል የመፍቀድ ስልጣን የለውም:: ግን ከሕግ ውጭ ሆኖ ሊከለክል ይችላል:: SO ተፈቀደ በማለት ፋንታ "መከልከሉን አቆመ! ወደ ሕግ ተመለሰ!" የሚሉትን ቃላት እንጠቀመ:: ሁሉም እሳቤ እና ጉዞ ከእሳቤ እና ከቃላት ይጀምራልና::

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Jan, 11:15


የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በዩኒቨርሲቲው በኒቃባቸው ምክንያት ከትምህርት ከምግብ እና ከመጠለያ እንዲገለሉ የተደረጉ ተማሪዎች እስከ ኒቃባቸው ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ከስምምነት ደረሰ!

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ላይ ላለፉት ወራት ሲደረግ የነበረውን መገፋት እና ጭቆና በሰላማዊ መንገድ ይፈታ ዘንድ ሲታገል እንደነበር አሳውቋል:: በተደረገው ሰላማዊ ትግል እና ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በተደረገ ውይይት በዛሬው እለት ላለፉት 10 ቀናት ከምግብ ከመጠለያ እና ከትምህርት በኒቃባቸው ምክንያት እንዲርቁ የተደረጉ ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃባቸውን ለብሰው ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሱ ዘንድ ከስምምነት እንደተደረሰ አሳውቋል:: ይህ ይመጣ ዘንድ ለመብታቸው የታገሉ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችና መላው ለሰብዓዊ መብት መከበር ትብብራቸውን ያሳዩ አካላትን በሙሉ አመስግኖም በዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ለደረሰውና ለሚደርሱ የመብት ጥሰቶች ሁሉ ፍትሕ እንዲሰፍን በማድረግ ረገድ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቋል::


©️ EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

26 Jan, 08:15


ድምጿ ይሠማ በሚል መሪ ቃል ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት የተዘጋጀ ፕሮግራም በይፋ ተጀምሯል። የህብረታችን ተወካዮችም በፕሮግራሙ ላይ እየታደሙ ይገኛሉ።

....

#ድምጿ_ይሠማ
#ድምጿ_ይሠማ

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

26 Jan, 03:45


ማዕቂል ኢብኑ የሳር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደዘገቡት- የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- “አንዳችሁ በብረት መርፌ ጭንቅላት ላይ መወጋቱ ለእርሱ የማትፈቀድለትን ሴት ከመንካት ይሻለዋል።"

ዑርዋ፣ አዒሻህ ሴቶች በምን መልኩ ለነብዩ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ቃል-ኪዳን ይገቡ እንደነበር ስታስረዳ እንደዚህ ማለቷን ዘግቧል- “የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) አንድም ሴት በእጃቸው አልነኩም። ለሴትየዋ ቃል-ኪዳኑ ምን እንደሆነ ይገልጹላትና ስትቀበል ‘ሂጂ ቃል ኪዳንሽን ሰጥተሻልና’ ይሏታል።” (ሙስሊም ዘግበውታል)

ከስህተት አላህ የጠበቃቸው፣ የሰው ልጆች ምርጥ የሆኑት፣ የአደም ልጆች መሪ የሆኑት ነብዩ እንኳን ሴቶችን አይነኩም ነበር። ታዲያ ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ውጪ ያለን ወንዶችስ?

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

25 Jan, 14:03


የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በወቅታዊ ጉዳዮች መግለጫ አውጥቷል!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

24 Jan, 19:21


🔴 “ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን ” - ሙስሊም ተማሪዎች

🔵 “ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማትን አስተዳደርና መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” - ዲላ ዩኒቨርሲቲ 

የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ እንዳይለብሱ በመከልከላቸው ከትምህርታቸው እየተስተጓጎሉ በመሆኑ መፍትሄ እንዲሰጣቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ በኩል ጠንከር ያለ ስሞታ አቅርበዋል።

የተማሪዎቹ ዝርዝር ስሞታ ምንድን ነው ?

“ ኒቃብና ጥቁር ማስክ እንዳንለብስ ነው የተከለከልነው። ክልከላው የጀመረው ከአንድ ወር በፊት ነበር። በዚህም ማመልከቻ አስገብተን ነበር መልበስ እንዲፈቀድልን። ሆኖም ግን ምላሽ ሳይሰጠን ቆዬ።

ትምህርታችን በስርዓት እንዳንከታተል አስተጓጎሉን። ቅዳሜ፣ አንዲት እህት ማስክ አድርጋ፣ ሂጃብ ለብሳ በምትገባበት ወቅት ኦዲያ ካምፓስ በሁለቱም በሮች እንዳትገባ ከልክለዋታል።

እንዲያውም ወንዶቹ የግቢው ጥበቆች አስፈራርተው ፊቷን አስከፍተዋታል። እንደዛም ሆኖ ማስክ ለብሳ ወደ ግቢ መግባት እንደማትችል ነግረው መልሰዋታል። 

ቅዳሜ ከሰዓት ሁለት ኒቃብ የለበሱ ተማሪዎች ግቢ ሊገቡ ሲሉ ተከልክለዋል። ለምን እንደተከለከሉ ሲጠይቁ ‘ ለደህንነት ሲባል ፊታችሁ መሸፈን የለበትም ’ አሏቸው።

ለደኅንነት ሲባል ከሆነ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በሴት ጥበቃ ተፈትሸው፣ አይዲያቸውን አሳይተው እንዲገቡ ሲጠይቋቸው ‘ ያንችን ፊት ማየት ምንም አይሰራልኝም። ፊትሽን ለምታሳይው አሳይ ’ የሚል መልስ ተሰጠን።

ከዚያ በኋላም ሰኞ እለት ደግሞ ኒቃብ፣ ጥቁር ማስክ መልበስ እንደማይቻል በፕሬዜዳንቱ ጭምር ተወሰነ። የተማሪ ተወካዮች ጠርተው ይህን አሳወቋቸው።

ጥበቃዎቹም ውሳኔውን በመጥቀስ ‘አናስገባም’ አሉን። ማክሰኞ እለት ማታ 44 ሴት ተማሪዎችን ‘ጥቁር ማስክ አድርጋችኋል አናስገባም’ ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን።

ረቡዕ ጠዋትም ከለር ማስክ አድርገው የገቡትን በፌደራል ጭምር አስፈራርተው ፊታቸውን እንዲገልጡ አድርገው፣ ሂጃብም ማውለቅ እንዳለባቸው አሳሰቧቸው።

ከሰኞ ጀምሮ ክላስም እየተከታተልን አይደለም፣ ኤግዛም አልፎናል፣ አሳይመንትም እያለፈን ነው። ማውለቅ ስለማንችል ከግቢ ውጪ ነን። በቃ ከተማሪነት ውጪ ባለ ህይወት ነን። እንደ ሴትነታችን ትልቅ የመብት ጥሰት ነው የተፈጸመብን። 

ከምሽቱ 3 ሰዓት እንዳንገባ ሲከለክሉን የት እንድናድር፣ ምን እንድንለብስ፣ ምን እንደምንምገብ ያሰቡትን አናውቅም። ስለዚህ እንደንገባ ቢፈቅዱም እንዲህ ያደርጉበት ምክንያትን ሊጠየቁ ይገባል ”
ሲሉ ተናግረዋል።

ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅናቸው ስማቸው እንዲነገር ያልፈቀዱ የዩኒቨርሲቲው አካል፣ ስለጉዳዩ በዩኒቨርሲቲው ፌስ ቡክ ገጽ የወጣውን መረጃ እንድንጠቀም ጠቁመዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተማሪዎቹ ነቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰው እንዳይገቡ ተከልክለው ከግቢ ውጪ በመሆናቸው ትምህርት እያለፋቸው እንደሆነ ገልጸዋል፤ መከልከሉ ልክ ነው ? የሚል ጥያቄ አቅርቧል።

በምላሻቸው፣ “ እንዲህ አይነት ነገር የለም። የተሳሳተ መረጃ ነው። ማንም ተማሪ እዚህ ግቢ በተፈቀደለት ሰዓት ይገባል፤ ይወጣል ” ሲሉ መልሰዋል።

“ የተቋሙንም ሆነ የትምህርት ሚኒስቴር የተቋማት አስተዳደር መመሪያዎችን ተከትሎ የሚተዳደር ነውና ተቋሙ ያንን ነው እያደረግን ያለነው ” ብለዋል።

ተማሪዎቹ በተጨባጭ ከግቢ ውጪ እንደሆኑ፣ ክላስ እያለፋቸው እንደሆነ በድጋሚ የገለጽንላቸው እኝሁ አካል፣ በድጋሚም “ የለም ” የሚል ማስተባበያ ነው የሰጡት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ የጌዴኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትን ተማሪዎች ደረሰብን የሚሉት ክልከላ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲው “ ሀሰተኛ መረጃ ነው ” ብሏልና እናንተ ጉዳዩን አይታችሁት ነበር ? ሲል ማረጋገጫ ጠይቋል።

ምክር ቤቱ ምን መለሰ ?

“ ጉዳዩ ከወር በፊት ደርሶን ነበር። እየቆየ ከፍ እያለ መጥቶ ተማሪዎች ግቢ ለመግባት ሲከለከሉ እኛም ደብዳቤ ፅፈን ነበር ችግሩ እንዲፈታ።

ዩኒቨርሲቲው እርከን ያልጠበቀ ጉዳይ ተደርጎ ታይቶ ነው፤ ተማሪዎቹን እናገኛቸዋለን የሚል ጥሩ ስሜት ነበረው። 

የእስልምና አለባበስ ከጥንት ጀምሮ ራሱን የቻለ ሊቃውንቶች ያስቀመጡት ነው። ይሄ የተሻለውና ተመራጭ የሆነው አለባበስ ነው ” ብሏል።


(ጉዳዩን የምንከታተለው ይሆናል)

©️tikvahethiopia

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

24 Jan, 08:15


በአሁን ሰዓት የፌደራል መጅሊስ አመራሮች ለውይይት የትምህርት ሚኒስቴር ይገኛሉ። ኸይር ያሰማን!

ነፃነት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

24 Jan, 04:13


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

23 Jan, 18:15


ሙስሊም ተማሪዎችን በአለባበሳቸው ምክንያት በየጊዜው ከትምህርት ገበታ ውጪ የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አሳሰበ!

- ሀሩን ሚድያ፣ ጥር 15/2017

የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በየጊዜው ሙስሊም ተማሪዎችን በሂጃብ እና በኒቃብ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ ለሚያደርጉ አካላት ቋሚ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቋል።

ጉባኤው በዛሬው ዕለት በሰጠው መግለጫ በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ለአብነትም በአክሱም እና በዲላ ዩንቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ ውጪ እንደተደረጉ በማንሳት የሚመለከተው የመንግስት አካል ይህን ኢ-ህገመንግስታዊ ተግባር ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጠው እንዲሰራ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ክልከላን ለምን አላወገዘም? ብለን "ሀሩን ሚድያ" ላቀረበላቸው ጥያቄም በየደረጃው ከሚገኙ የመንግስት አካላት ጋር ውይይት እያደረግን ስለነበር ነው ዝም ያልነው ያሉ ሲሆን ጉዳዩ በቅርቡ እልባት ያገኛል ብለው እንደሚያስቡም ገልጸዋል።

በዛሬው መግለጫ ላይ ጥቂት ግለሰቦች እና ቡድኖች የሌሎች እምነት ተከታይ ወገኖችን ልብስ በመልበስ የእምነቱ ተከታዮችን ለማስቆጣት የሚያደርጉት ተግባር አግባብነት የሌለው በመሆኑ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራን ነው ብለዋል።

የኢስላማዊ አለባበስ መገለጫ የሆነውን ጀለቢያ በመልበስ ሙስሊሞች በመምሰል የትንኮሳ ስብከቶችና ዝማሬዎች በማቅረብ፣ የትንኮሳ አለባበሶች ጭምር በመጠቀም በማኅበራዊ ድረገጽ የለቀቁት አጫጭር ቪዲዮች የእምነቱ ተከታዮችን ማስቆጣቱና በፅኑ እንደሚወገዝ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሀፊ ተናግረዋል ::

© ሀሩን ሚድያ

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

23 Jan, 14:40


"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነገረኛ ወሬን ቢያመጣላችሁ በስህተት ላይ ኾናችሁ ሕዝቦችን እንዳትጎዱና በሠራችሁት ነገር ላይ ተጸጸቾች እንዳትኾኑ አረጋግጡ፡፡" (አል-ሑጁራት 6)

ዛሬ ከዙህር ጀምሮ ከላይ ያለው ምስል ብዙ ተከታይ ባላቸው ቻናሎችና ግሩፖች ጭምር ሲሰራጭ አስተውለናል። የመስጂዱ ጀመዓዎችም ጉዳዩን ለማብራራት የሞከሩ ቢሆንም ያዳመጣቸው አልነበረም።

ለማንኛውም ጉዳዩ እንዲህ ነው፦
የቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 6 አመራሮች ታቦት የሚወጣበትን ሰዐት ጠብቀው በቄራ መስጂድ ስም ከላይ ያለውን ባነር አሰርተው በቄራ መስጂድ አጥር ያለማንም እውቅና እና ፈቃድ ለጥፈው የመስጂዱን ክብር ደፍረዋል። የመስጂዱ አስተዳደሮች ጉዳዩ እንደደረሳቸው ጉዳዩን በማጣራት ባነሩን ወዲያው ያነሱት ሲሆን ይህንን ባደረጉ አካላትም ላይ ክስ እንደሚመሰርቱ አሳውቀዋል። አላህ ያግዛቸው! ጥጋበኞችንም የአላህ ቅጣት ይውረድባቸው!

ነገር ግን በዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ አንድ የታዘብነው ነገር እስካሁን በኸይር የምናውቀውን መስጂድ እና ጀመዓ በቅጡ ባልተጣራ ጉዳይ ታላላቅ ከምንላቸው ሳይቀር ትችቶችን ታዝበናል። የሙዕሚን ቀልብ አላህ ዘንድ ከዱንያ እና በዱንያ ውስጥ ካሉ ነገሮች ሁሉ የበለጠ ዋጋ አለውና ያለአግባብ ወንድሞቻችንን ከመተቸት መጠንቀቅ ያስፈልጋል።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

23 Jan, 14:04


የፌደራል መጅሊስ ስለ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ ፅፏል:: የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በአፋጣኝ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ብሎም ችግሩን በሀገር አቀፍ ደረጃ በዘላቂነት እንዲፈታ ሲል አሳውቋል::

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

23 Jan, 08:08


ዲላ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲው ኒቃቢስት መምህራንንም በኒቃብ መግባት እና ማስተማርን ከለከለ!

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለአመታት እስልምናዋ የሚያዛትን ኒቃብ ለብሳ ስታስተምር የነበረች ሌክቸር ከትላንት ጀምሮ "ወይ ስራሽን ወይ ኒቃብሽን ምረጪ?" የሚል ትዕዛዝ እንደተላለፈላት ተገልፇል:: "ስራዬንም እምነቴንም ይዤ እቀጥላለሁ!" የሚል መልስ ብትሰጥም ለመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እና ክልከላ በዛሬው እለት ጠርተዋታል::

በተማሪዎቹ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ አይበቃው ያለው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ወደ እስታፍ ሰራተኞችም ተሸጋገረ:: ይህ ግልፅ የሆነ ሙስሊም ጠልነት ነው:: አዳጊ ወጣቶችን ከግቢ ውጭ ያለምግብ ያለትምህርት ያለማደሪያ የሚያሳድረው ተቋም የሀገሪቱን እናቶችንም በእምነት እየለዬ ማስለቀሱን ጀመረ::

ይህ አውሬያዊ ጭካኔ የተሞላበት ግፍ ነው!

ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም መምህራን!
ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ማህበረሰብ!
ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!
ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች!

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

23 Jan, 07:11


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በዲላ ዩኒቨርሲቲ እየተፈፀመ ስላለው የመብት ጥሰት ለፌደራል መጅሊስ ደብዳቤ ጻፈ!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

23 Jan, 06:20


"አላህንም በደለኞች ከሚሠሩት ግፍ ዘንጊ አድርገህ አታስብ፡፡ የሚያቆያቸው ዓይኖች በእርሱ እስከሚፈጡበት ቀን ድረስ ብቻ ነው፡፡" (ኢብራሂም 42)

ይህ ኢትዮጵያ ውስጥ በዲላ ከተማ ነው። ኒቃቢስቶቹን እስከዛሬ ገብተው ሲማሩበት ሲኖሩበት ከነበረው ግቢ በጨለማ ያለምንም ርህራሄ አትገቡም ብለው ሲመልሷቸው ይታያል።

መብቱን በልመና ሳይሆን በትግል የሚያስከብር ትውልድ እንደመጣ አላወቁም!

ኢንሻላህ በአላህ ፈቃድ በጣም በቅርብ ጊዜ በኢትዮጵያ የሙስሊም ተማሪዎች መብት ተከብሮ የሚማሩበት ሁኔታ ይፈጠራል! ኢንሻላህ በAAU ያለው በደል በቅርቡ ይቆማል! ኢንሻላህ በዲላ ያለው በደል በቅርቡ ይቆማል! ኢንሻላህ በሰላሌ ያለው በደል በቅርቡ ይቆማል! ኢንሻላህ በጂማ ያለው በደል በቅርቡ ይቆማል! በጣም በቅርቡ ኢንሻላህ!!!

ሁላችንም ለትግሉ ራሳችንን እናዘጋጅ!! መረጃዎችን እናሰራጭ! መብታችን በልመና ሳይሆን በትግል እናስከብር

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

21 Jan, 03:47


ኢብኑ አቢ ለይላ ከሱሐይብ እንዳስተላለፉት፣ የአላህ መልዕክተኛ (ሰለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡-

"የአማኝ ሁኔታ የሚደንቅ ነው፤ ሁኔታው ሁሉ ለርሱ ጥሩ ነው፤ ይህ ደግሞ ከአማኝ በስተቀር ለማንም አይደለም። ጥሩ ነገር ቢደርስበት አመስጋኝ ነው፤ ይህም ለእሱ ጥሩ ነው። መጥፎ ነገር ቢደርስበት ደግሞ ታጋሽ ነው፤ ይህም ለእሱ ጥሩ ነው።" (ሙስሊም ዘግበውታል)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Jan, 18:36


ዲላ ዩኒቨርሲቲ ••• Update!

የዲላ አናብስቶች 3ኛ ቀናቸውን በእምቢታ ቀጥለዋል:: ዛሬም ኒቃብ ለብሳችሁ ከግቢ አትገቡም የተባሉት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስት እህቶቻችን ከግቢ ውጭ ከመስጂድ አድረዋል:: በሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ ግብር የተነባ የልሕቀት ማዕከል የሀገሪቱ ግማሽ የሆነውን ሙስሊም ማህበረሰብ ልጆች በእምነታቸው ሳቢያ ማደሪያ እንኳን ነፍጎ ከውጭ ያሳድራል::

በአላህ ፈቃድ ግን ይህን መሠሉ በራስ ሀገር በራስ ተቋም የሚፈፀም ግፍ ፍፃሜውን ያገኛል ••• ነፃነት በነፃ አይገኝም!

©️EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Jan, 10:59


"ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ስለሆነ መልበስ አይቻልም!" - ዲላ ዩኒቨርሲቲ

ላለፉት 3 አመታት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ በነፃነት ይለበስ የነበረውን ኒቃብ ያለ ሕግ እና መመሪያ ከወር በፊት ከልክሎ የነበረው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር ግብግብ ውስጥ እንደነበር ይታወቃል:: በሰሞኑም ለብሳችሁ አትገቡም በማለቱ ሙስሊም ተማሪዎች ከግቢ ውጭ ከመስጂድ ማደራቸው ይታወሳል::

የተፈጠረውን ችግር ለመፍታትም በዛሬው እለት ከሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረገው የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር "ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ስለሆነ በግቢ ውስጥ ለብሶ መግባትም ሆነ መንቀሳቀስ አይቻልም!" የሚል መልስ እንደሰጣቸው ተማሪዎች አሳውቀዋል::

በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተጨባጭ ያልሆነ እና እምነቱን የሚዳፈር ምክንያት በማቅረብ የሚደረግ የመብት ጥሰት መቆም እንዳለበት:: ኒቃብንም ሆነ የትኛውንም ኢስላማዊ አለባበስ የደህንነት ስጋት አድርጎ ማሰብም ሆነ ማቅረብ ሀይማኖቱን ከማንቋሸሽ ተለይቶ አይታይም:: ኒቃብ በሐይማኖት እንዲለበስ የታዘዘ የእምነት ልብስ ሲሆን በሕግ ደግሞ የማይከለከል የነፃነት መገለጫ ነው::

በአላህ ፈቃድ መሠል ጥላቻ ተኮር የመብት ጭቆናዎች በዚህ ትውልድ ታሪክ ይሆናሉ ••• ነፃነት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም!

©️EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

19 Jan, 19:52


ሰዎች በዑመር ቤት ተሰብስበዋል፤ ሁሉም እያለቀሱ ነው። የሙስሊሞች መሪ፣ ጀግናውና ቆፍጣናው ዑመር ፈጅር ሊያስግዱ በገቡበት 7 ቦታ ተወግተው ራሳቸውን ስተው ወድቀዋል። ዑመር ወደቤታቸው ተወሰዱ፤ በከፍተኛ ሁኔታ እየደሙ ነው፤ ራሳቸውን ስተዋል።

እንደነቁም በዙሪያቸው ያሉትን ሰዎች ባዩ ጊዜ በመጀመሪያ የተናገሩት ነገር "ሰዎች ሰግደዋልን?" ነበር። እንደሰገዱም ሲነገራቸው “ሰላትን ለተወ ሰው በእስልምና ውስጥ ድርሻ የለውም" አሉ። ከዚያም ቁስላቸው እየደማ ውዱእ አድርገው ሰገዱ።

የኛ ሰለፎች እነዚህ ነበሩ፤ የሞት አፋፍ ላይ ሆነው እንኳን ጭንቀታቸው ሁሉ ሰላት ነበር። እኛስ? በሚረባው በማይረባው የሰላትን ሰዓት የምናሳልፍ፤ ከነጭራሹም የምንተዉ ሰዎች? ዑመር እኛ ያለንበትን ሁኔታ ቢመለከቱ ምን ይሉ ነበር?

አላህ ያስተካክለን!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

19 Jan, 05:58


ጥቆማ!

የሳኡዲ አረቢያ ኤምባሲ የባህል ዘርፍ 2ተኛ ዙር ሀገር አቀፍ የወንዶች እና የሴቶች ሀዲስ ሂፍዝ ዉድድር አዘጋጅቷል። በዚህኛው ዙር ለውድድር የቀረበው ኪታብ በሰሚር ኢብኑ አሚር አልዙሀይሪ አርትኦት የተዘጋጀው የኢብኑ ሀጀር አል አስቀላኒ ቡሉገ-ል-መራም ሚን አዲለቲ-ል-አህካም ነው።

📌 የመፅሐፉ PDF: https://down.ketabpedia.com/files/bkb/bkb-ha1853-ketabpedia.com.pdf

📌 የመወዳደሪያ ደረጃዎች (አንድ ሰው በአንድ ደረጃ ብቻ ነው መወዳደር የሚችለው)
1. 1 - 57 ያሉ ሀዲሶችን መሐፈዝ
2. 1 - 108 ያሉ ሀዲሶችን መሐፈዝ
3. 1 - 150 ያሉ ሀዲሶችን መሐፈዝ
4. 1 - 203 ያሉ ሀዲሶችን መሀፈዝ

📌 ለውድድሩ መስፈርቶች
1. ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ መሆን፤
2. እድሜ ከ 40 አመት በታች መሆን፤
3. በፈተናው ቀን፣ ሰዓት እና ቦታ መገኘት መቻል፤
4. የምግብ፣ የማደሪያ፣ የትራንስፖርትና ማንኛውም ወጪ በራሳቸው መሸፈን መቻል፤


📌 ለመመዝገብ በዋትስአፕ ቁጥር:-
- ለወንዶች +251928933333
- ለሴቶች +251945777744
+251945777755

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

19 Jan, 03:27


"ተጸጽቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡ እነዚያም አላህ መጥፎ ሥራዎቻቸውን በመልካም ሥራዎች ይለውጣል፡፡ አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው፡" (አል-ፉርቃን 70)

ሰዎች በምታደርገው አንድ መጥፎ ነገር ምክንያት መልካም ታሪክህን ሙሉ በሙሉ ያጠፉታል፤ አላህ ግን በአንዲት ቅን ተውባህ (ንሰሀ) ምክንያት የመጥፎ ታሪክህን ሰርዞ ወደ መልካም ይለውጣል።

ተጸጽቶ የተመለሰን ሰው ወንጀል የሚምር ብቻ ሳይሆን በመልካም ስራዎች የሚለውጥ የሆነው አሏህ ጥራት ይገባው።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Jan, 19:01


አስከፊውን ጦርነት እና በፍልስጤማውያን ላይ እየደረሰ የነበረውን ጭፍጨፋ ሊያስቆም የሚችል ስምምነት እንደተፈረመ እየሰማን ነው።

አሏህ ይህን የፍልስጤማውያን የስቃይ መጨረሻ ያድርግላቸው፤ በነርሱ ላይም አሏህን የሚፈሩና በርሱ ህግ የሚያስተዳድሩ መሪዎችን ይሹምlላቸው፤ ሐገራቸውንም ከወራሪዋ ነጻ ያድርግላቸው፤ ወደሐቅ የዘነበሉና ለሐቅ ተገዥ የሚሆኑም ያድርጋቸው!

የወንድሞቻችን ስቃይ እንዲያበቃ ሊያደርግ የሚችል ስምምነት መፈረሙ ቢያስደስተንም ነገር ግን ደስታችንን በልክ ማድረግ ይገባል። አሏህ ስለአይሁዶች እንዲህ ብሏል፦ "ቃል ኪዳንንም ቃል በገቡ ቁጥር ከእነርሱ ከፊሉ ይጥለዋልን? (ያፈርሰዋልን?)፤ ይልቁንም አብዛኞቻቸው አያምኑም፡፡" (አል-በቀራህ 100)። በታሪክ ያየነውስ ይሄንኑ አይደለምን?

ጌታችን አሏህ ሆይ የፍልስጤማውያንን ሰላም ዘላቂ አድርግላቸው፤ ሙታኖቻቸውን ከሹሃዳኦች መካከል ተቀበላቸው፤ ያሉትን አጠንክራቸው!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Jan, 18:47


ማስታወሻ!

ነገ ሐሙስ ነው። የቻልን እንጹም፤ ያልቻልን መልዕክቱን እናሰራጭ!

عن عائشة رضي الله عنها قالت : كان النبي صلى الله عليه وسلم يتحرَّى صوم الإثنين والخميس
ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዓንሃ) እንዲህ ብላለች፦ "ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሰኞና ሐሙስ መጾምን ያዘወትሩ ነበር" (ቲርሚዚ፤ ኢብኑ ማጃህና ነሳኢ ዘግበውታል)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

12 Jan, 19:48


ከነገ ጀምሮ ያሉት 3 ቀናት አያመል ቢድ ናቸው። ነብዩ (ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰላም) አዘውትረው የሚጾሟቸውና ለኡማቸውም ጹሟቸው ብለው የመከሯቸው ቀናት ናቸው። የመጀመሪያው ቀን ሰኞ ነው። ሰኞን መጾም ራሱን የቻለ ሱንና ነው። ስለዚህ ድርብርብ መልካም ስራ መፈጸም የሚቻልባቸው ቀናቶች ከፊታችን ተደቅነዋልና እንጠቀምባቸው።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

12 Jan, 19:38


በነገው ዕለት final exam የምትጀምሩ ወንድምና እህቶች ሁሉ መልካም እድል እንመኛለን።

አላህ ፈተናችሁን ያገራላችሁ ዘንድ ዱዓችን ነው፤ ካሰባችሁት በላይ ያቅልልላችሁ፤ ጥሩን ውጤት ይወፍቃችሁ፤ በሰላም ጀምራችሁ በሰላም የምትጨርሱ ያድርጋችሁ።

ፈተናውን ጀምራችሁ እስከምትጨርሱ ኢስላማዊ አደብ እና ስነ-ምግባር ትላበሱ ዘንድ እና ለጊዜያዊ ጥቅምና ደስታ ብላችሁ ጌታችሁን የሚያስቆጣ ድርጊት ከመፈጸም ትቆጠቡ ዘንድ አደራችን ነው!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

12 Jan, 08:06


ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በሙስሊም ተማሪዎች ላይ በተደጋጋሚ እየደረሱ ባሉ የመብት ጥሰቶች ዙሪያ የተሰጠ የአቋም መግለጫ።

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

11 Jan, 06:52


عن عمر بن الخطاب رضي الله عنه : أن النبي صلى الله عليه وسلم قال: «إن اللهَ يَرفعُ بهذا الكِتابِ أقْواماً ويَضَعُ به آخَرِينَ».

ዑመር ኢብኑል ኸጣብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፉት ነቢዩ (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- “በእርግጥ አላህ በዚህ መጽሐፍ (ቁርዓን) የተወሰኑ ሰዎችን ከፍ ያደርጋል ሌሎችን ደግሞ ያዋርዳል።" (ሙስሊም ዘግበውታል)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Jan, 03:24


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

06 Jan, 08:54


በነገው ዕለት በካፌ ስለሚዘጋጀው ምግብ ጉዳይ!

ብዙ ጊዜ በዩኒቨርሲቲዎች ዉስጥ በካፊሮች በአላት ስለሚዘጋጁ ምግቦች ውዝግቦች ይስተዋላሉ። የካፊሮች በዓላት በደረሱ ቁጥር ጉዳዩ የክርክር እና የጭቅጭቅ መንስዔ ይሆናል።

በመጀመሪያ የካህዲያንን በአላት ማክበርም ሆነ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት ማስተላለፍ በጥብቁ የተከለከለ ነው። በዚያ እለት የሚያዘጋጁትን ምግብ ሄዶ መመገብም በተመሳሳይ ይከለከላል። በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም ውዝግብ የለም።

ነገር ግን በዩኒቨርሲቲ ካፌዎች የሚዘጋጀው ምግብ ከካህዲያን ዘንድ ሄዶ ከመብላት ስለሚለይ በተወሰነ ደረጃ ውዝግብ ያለበት ጉዳይ ነው። በጉዳዩ ላይ በአጠቃላይ ሁለት አስተያየቶች አሉ።

የተወሰኑ ኡለሞች ይህንን ምግብ መመገብ ለሙስሊሞች የማይፈቀድ በዓል አካል መሆንን ስለሚያሲዝ ሙሉ በሙሉ ክልክል እንደሆነ አስቀምጠዋል። የአንድ በዓል ዋና መገለጫው ለርሱ ተብሎ የሚዘጋጀው ምግብ በመሆኑና ዩኒቨርሲቲዎችም ይህንን ምግብ የሚያዘጋጁት በዓሉን ለማክበር በመሆኑ ይህንን መመገብ የበዓሉ ተሳታፊ መሆን ነውና በምንም መልኩ ሊመገቡ አይገባም ይላሉ።

ሌሎች ኡለሞች ደግሞ በዩኒቨርሲቲው የሚቀርበውን ምግብ መመገብ ተማሪዎች ከሚገባቸው የእለት ተእለት አቅርቦት አካል ስለሆነ ማክበርን አያመጣም በማለት መመገቡ ምንም ችግር እንደሌለው አስቀምጠዋል። ይህ ልክ በሌሎች ቀናት ሙስሊም ባልሆኑ ምግብ ቤቶች የሚመገብ ሰው በበዓላቸውም ቀን በዓሉን ለማክበር እስካላሰበ ድረስ እዚያ መመገብ እንደሚችለው አይነት ሁኔታ ነው ይላሉ። በተጨማሪም፣ ተማሪዎች ለዚህ ምግብ ተመገቡም አልተመገቡም በወጪ መጋራት ክፍያ የሚከፍሉ በመሆናቸው፣ መብታቸውን እንደሚያሟላ እንጂ በበዓሉ ላይ እንደመካፈል አይታይም ይላሉ።

ነገር ግን በአጠቃላይ እንደ ሙስሊም ከአጠራጣሪ ጉዳዮች ላይ ጥንቃቄ የማድረግ ግዴታ አለብን። ነብዩ (ሶለሏሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፡- "የተፈቀዱ ነገሮች ግልፅ ናቸው፣ ሀራምም ግልፅ ነው፣ በመካከላቸውም ብዙ ሰዎች የማያውቁት አጠራጣሪ ጉዳዮች አሉ፣ አጠራጣሪ ጉዳዮችን የራቀ ሰው ከዲኑ እና ከክብሩ አንፃር እራሱን አድኗል።" ብለዋል። በሌላም ሀዲስ "የሚያጠራጥርህን ለማያጠራጥርህ ነገር ተወው" ብለዋል። ከነዚህ ሐዲሶች እንደምንረዳው አሻሚ በሆኑ ሁኔታዎች ውስጥ ጥንቃቄ ማድረግ ነብያዊ አስተምህሮ እና ሱና ነው።

ለዚያ ቀን አማራጭ ምግብን ማግኘት የሚችል ሰው ራሱንም ዲኑን ከጥርጣሬ ይጠብቅ፤ ሌሎች አቅሙ የሌላቸውን ወንድሞቹንም ይገዝ!!

ነገር ግን ጥንቃቄ ማድረግ የተሻለ ቢሆንም እንደዚህ ባሉ አወዛጋቢ ጉዳዮች ተነስቶ ሌሎችን መዝለፍም ሆነ መተቸት ተገቢ አይደለም፤ ጉዳዩ የውዝግብ ጉዳይ እስከሆነ ድረስ አንዱ ለሌላው ዑዝር ሊሰጥ ይገባል።

አላህ (ሱበሐነሁ ወተዓላ) ወደ ወደደው ነገር ይመራን ዘንድ፤ ሐቅ ከባጢል ግልፅ ያደርግልን እና አጠራጣሪ ጉዳዮች ውስጥ ከመውደቅ ይጠብቀን ዘንድ እንለምነዋለን!

ወላሁ ኣዕለም

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

05 Jan, 06:01


رِجَالٌۭ لَّا تُلْهِيهِمْ تِجَـٰرَةٌۭ وَلَا بَيْعٌ عَن ذِكْرِ ٱللَّهِ وَإِقَامِ ٱلصَّلَوٰةِ وَإِيتَآءِ ٱلزَّكَوٰةِ ۙ يَخَافُونَ يَوْمًۭا تَتَقَلَّبُ فِيهِ ٱلْقُلُوبُ وَٱلْأَبْصَـٰرُ

"አላህን ከማውሳትና ሶላትን ከመስገድ ዘካንም ከመስጠት ንግድም ሽያጭም የማያታልላቸው ልቦችና ዓይኖች በእርሱ የሚገላበጡበትን ቀን የሚፈሩ የኾኑ ሰዎች (ያጠሩታል)፡፡" (አል-ኑር 37)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

03 Jan, 19:03


ወንድማዊ ምክር!

"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በዐርብ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት ኺዱ፡፡ መሸጥንም ተዉ፡፡ ይህ የምታውቁ ብትኾኑ ለእናንተ በጣም የተሻለ ነወ፡፡" (አል-ጁሙዓ 9)

የጁምዓ 2ኛው አዛን ከወጣ በኃላ ምንም አይነት ንግድ ማድረግ ሐራም ነው። ብዙዎቻችን አዛን ከተባለ በኃላ ፔስታል፤ የጥርስ መፋቂያ እና ሌሎች ነገሮችን እንገዛለን! ይህ አላህ የጁምዓ ጥሪ ከተደረገ በኃላ "መሸጥንም ተዉ" በማለት ያዘዘንን ትዕዛዝ በግልጽ መቃረን ነው። ሊስተካከል ይገባል!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

03 Jan, 03:23


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

02 Jan, 13:40


የሙስሊሙን ማኅበረሰብ ሐይማኖታዊ ግዴታዎችንና መገለጫዎችን ማንኛውም አካል ወይም ግለሰብ መከልከልም ሆነ ማደናቀፍ እንደሌለበት እናሳስባለን፡፡

- የዑለማእ ጉባኤ ፈትዋ ፅ/ቤት

▣ ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 24/2017

ሙስሊም ሰራተኞች፣ እንዲሁም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ማለትም በዩኒቨርሲቲዎችና በተለያዩ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች እና ስራተኞች በሃይማኖቱ ግዴታ የሆኑት ሶላትንና ሂጃብን አስመልክቶ በተደጋጋሚ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮችን አስመልክቶ የዑለማእ ጉባኤ የፈትዋ ጽ/ቤት ፈትዋ ሰጠ!

የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዐለማእ ጉባኤ የፈትዋ ጽ/ቤት እንደገለፀው በተለያዩ የመንግስትና መንግስታዊ ባልሆኑ መስሪያ ቤቶች ተቀጥረው የሚሰሩ ሙስሊም ሰራተኞች፤ እንዲሁም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ማለትም በዩኒቨርሲቲዎችና በተለያዩ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎች እና ስራተኞች በሃይማኖቱ ግዴታ የሆኑት ሶላትንና ሂጃብን አስመልክቶ በተደጋጋሚ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች ፈትዋ እንዲሰጥበት ጥያቄ መቅረቡን ገልጿል፡፡

ስለሆነም ይህ ጉዳይ፦

1. የእለት ተዕለት ሶላትን በተመለከተ፦

1.1 አላህ (ሱ.ወ) በተከበረው ቁርኣን በ 5ኛው ምዕራፍ በ103ኛው አንቀጽ ላይ - ሶላት በምዕመናን ላይ በጊዜ የተወሰነች ግዴታ ናት ይላል፡፡ ስለዚህ ማንኛውም ሙስሊም አምስት ወቅት ሶላት ከደረሰበት በየትኛውም ቦታ መስገድ ግዴታ አለበት፡፡

1.2 የጁምዓ ቀን ሶላትን በተመለከተም፦

አላህ (ሱ.ወ) በተከበረው ቁርኣኑ በ62ኛው ምዕራፍ በ9ኛው አንቀጽ «እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በአርብ ቀን ለጁምኣ ጥሪ በተደረገ ጊዜ ወደ አላህ ማውሳት (ኹጥባ ለማዳመጥ ለሶላት) ሂዱ፡፡መሸጥንም ግብይትንም ተዉ» ይላል፡፡ ስለዚህ የጁምዓ ሶላት የደረሰበት ሰው ወደ መስጂድ ሂዶ መስገድ ግዴታው ነው፡፡

2. ሂጃብን በተመለከተ፦

አላህ (ሱ.ወ) በተከበረው ቁርኣን በ33ኛው ምዕራፍ በ59ኛው አንቀጽ ላይ «አንተ ነብይ ሆይ!ለሚስቶችህ! ለሴቶች ልጆችህም፤ ለምዕመናን ሴቶችም፣ ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው» ይላል፡፡

ስለሆነም ማንኛዋም ሙስሊም ሴት በማንኛውም ቦታና ሁኔታ እስላማዊ አለባበስን የመጠበቅ ግዴታ አለባት ፡፡ በአጠቃላይ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ሐይማኖታዊ ግዴታዎችንና መገለጫዎችን ማክበርና መተግበር ግዴታ እንዳለበት እያሳሰብን ማንኛውም አካል ወይም ግለሰብ ይህንን የፈጣሪያችንን ግዴታ (ትዕዛዝ) መከልከልም ሆነ ማደናቀፍ እንደሌለበት እናሳስባለን፡፡

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ስር ያሉ ሁሉም መዋቅሮች ይህንን ጉዳይ በንቃት መከታተል እንዳለባቸው የኡለማዎች ጉባኤ ፅህፈት ቤት ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

© ሀሩን ሚድያ

AAU - Muslim Students Union

01 Jan, 11:02


ሳትማር የምትቀርበት ብቸኛ ነገር ዲንህ እንዲሆን አትፍቀድ!

ወደ ዩኒቨርሲቲ ገብተሃል ያውም በኢትዮጵያ አንጋፋ የሚባለው ዩኒቨርሲቲ፤ ብሩህ እና ለትምህርት ቁርጠኛ ነህ። ሳትማር የምትቀርበት ብቸኛ ነገር ዲንህ እንዲሆን አትፍቀድ።

"ከቅርቢቱ ህይወት ግልጹን ብቻ ያውቃሉ፡፡ እነርሱም ከኋለኛይቱ ዓለም እነርሱ ዘንጊዎች ናቸው፡፡" (አር-ሩም 7)

"አላህ የዱንያን እውቀት ዐዋቂ የሆነን ግን የአኼራን እውቀት የማያውቅ ሰውን ይጠላል።" (ሰሒሕ ኢብን ሒባን)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

29 Dec, 19:30


ማስታወሻ!

ነገ ሰኞ ነው። የቻልን እንጹም፤ ያልቻልን መልዕክቱን እናሰራጭ!

عن عائشة رضي الله عنها قالت : كان النبي صلى الله عليه وسلم يتحرَّى صوم الإثنين والخميس
ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዓንሃ) እንዲህ ብላለች፦ "ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሰኞና ሐሙስ መጾምን ያዘወትሩ ነበር" (ቲርሚዚ፤ ኢብኑ ማጃህና ነሳኢ ዘግበውታል)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Dec, 14:35


በዛሬው እለት በ6 ኪሎ ጀመዓ አዘጋጅነት በአል-አቅሷ መስጂድ በተካሄደው የዳዕዋ ፕሮግራም ላይ ከተማሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎች የተመለሱ መልሶች

🎙 በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Dec, 14:34


📌 ምክር ለተማሪዎች
🎙 በኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር

በዛሬው እለት በ6 ኪሎ ጀመዓ አዘጋጅነት በአል-አቅሷ መስጂድ በተካሄደው የዳዕዋ
ፕሮግራም ላይ የተላለፈ ወሳኝ መልዕክት

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Dec, 14:32


📌 ጾታዊ ፈተናን መከላከል
🎙 በኡስታዝ አቡል አባስ ናስር ሙሐመድ

በዛሬው እለት በ6 ኪሎ ጀመዓ አዘጋጅነት በአል-አቅሷ መስጂድ በተካሄደው የዳዕዋ
ፕሮግራም ላይ የተላለፈ ወሳኝ መልዕክት

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

27 Dec, 08:02


📢 ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም (2 ቀን ቀሪው)

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የ6ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በ3ተኛው ዙር የደዕዋ ፕሮግራማችን በአይነቱ ልዩ የሆነ የሴሚስተር መዝጊያ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።

የእለቱ ተጋባዥ እንግዶች፦
💠 ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
💬 ምክር ለተማሪዎች

💠ኡስታዝ አቡል ዓባስ
💬ፆታዊ ፈተናን መከላከል

በእለቱ በጣፋጭ ሙሓደራዎቹ እና በስል ብዕሩ ከምናውቀው ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር እና በባለፈው አመት አስደሳች ኮርስ ከሰጠን ኡስታዝ አቡል ዓባስ ጋር የማይረሳ ጊዜን እናሳልፍ።

📍እንዲሁም በፕሮግራሙ በሴሚስተሩ አመርቂ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች አካዳሚክ ሴክተር ሽልማት ያበረክታል።

ቀን: ቅዳሜ ማለትም 19/04/2017
ሰዐት፡ከዙሁር ሶላት በኋላ
ቦታ፡ አል-አቅሷ መስጂድ(አጅሩሚያ ክፍል)

©AAU-MSU 6kilo Jemea ዳዕዋ እና ቂርዓት ሴክተር

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

27 Dec, 08:02


📢 Sagantaa muhaadaraa addaa

Jama'aan barattoota Muslimaa Yuunivarsiitii Finfinne kiiloo 6 sagantaa cufaati Seemistera fi muhadaraa marsaa 3ffaa isiini qopheesse jira.

  Keessummoonni keenya:
  💠 Ustaaz Ibnu Munawwar
            💬 Gorsa barattootaaf

  💠Ustaaz Abul Abbaas
            💬 Qormaata saala faallaa ittisu

Qophii kanatti Gorsa mi'aawaa fi barreeffama isaatin kan beekkamu Ustaaz Ibnu Munawwar kan muhaderaa fi qalama  ta'een beeknu fi kan bara darbe barnoota hawwataa kan nuuf kenne Ustaaz Abul Abbaas waliin yeroo midhagaa fi bu'aa qabeessa haa dabarsinu isiini jeenna.

📍Akkasumas saganticharratti barattoota seemstera bara darbeen qabxii gaarii galmeessisaniif badhaasa isaanif qophaa'e ni laatamaaf.

Guyyaa: Sanbata 19/04/2017
Yeroo: Salaata Zuhrii booda
Iddoo: Masjiida Al-Aqsaa (Kutaa Ajrumiyaa).


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

27 Dec, 05:35


ሰዓታት ብቻ ቀሩት!

በ5ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚዘጋጀውና በዓይነቱ ልዩ የሆነው ቀዋዒድ ተከታታይ የደውራ ፕሮግራም የመጀመሪያ ዙር ፕሮግራም ሰዓታት ብቻ ቀርተውታል!!

በመጀመሪያ ዙር ፕሮግራምም፦
- ተጋባዥ ኡስታዝ፡ ኡስታዝ አብዱሰላም ረሺድ
- ኪታብ፡ መንዙመቱ አሕሰኒል-አኽላቅ

ሰዓት፡ ዛሬ ጁምዓ ታህሳስ 18፤ ከዐስር ጀምሮ
ቦታ፡ አል-አቅሷ መስጂድ (አጅሩሚያ ክፍል)

የተመዘገባችሁ ከናንተ የሚጠበቀው ብዕር እና ማስታወሻ ይዞ መምጣት ብቻ ነው። Hardcopy እዚያው የምትሰጡ ይሆናል።

©️fivekjemaa

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

26 Dec, 20:27


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Dec, 13:51


After a long wait and some delays, the time has come – Qalam Q & A Competition officially kicks off tonight at 3:00 PM local time!

Reminder: Registration closes tonight at 3:00 PM local time, so if you haven’t signed up yet, this is your last chance to join!

A helpful tip: 60% of the questions are drawn directly from the reading materials we’ve shared. Take some time to review them thoroughly and give yourself the best chance to excel.

Registration link: https://forms.gle/gqVoNDphT3ekdAEk6
Reading material: https://t.me/AAU6kilojemea/1297

©️AAU-MSU 6-kilo Jemea

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Dec, 13:50


የ6 ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመአ አመራሮች  ወደ ቢሾፍፈቱ ቄራ በአካል በመሄድደ የእርድ ሂደቱን ጎበኙ።

ከተማሪዎች ካውንስል ህብረት ጋር የተካሄው ይህ ጉብኝት ለ Bishoftu veternary campus ድንገተኛና ምንም አይነት መልክት ሳይሰጣቸው የተደረገ ነበር።
ይህን ጉብኝት ስናደርግ የካምፓሱ ዲን የሆኑት Dr. Hika እና የካምፓሱ ፋስሊቲ ሀላፊ Dr. ቀጄላን ማናገር ችለናል።

Dr. Hika እንዳሉት፦ "ጊቢው ከአመታት በፊት ሚያቀርበውን ስጋ ከከተማ ቄራ ውስጥ ሲያሳርድ ቆይታል ቢሆንም ግን ከጊዜ ቡሃላ የተለያዩ ጥርጣሬዎችን በማስተዋሉ ምክንያት የእርድ አቅርቦት ስራ ለቢሾፍቱ ካምፓስ እንደ ሃላፊነት ተሰጥተል። በመሆኑም ከአራት አመታት በፊት  ሙስሊም ተማሪዎችን በማስጠራት ሃላል የማድረጉን ስራ ሲሰሩ ቆይተዋል። ከአራት አመት ወዲህ ባለው አሰራር ደሞ ጫረታ በማውጣት ለአንድ አመት በሚቆይ ኮንትራት በሙስሊም አራጆች ስራው እየተካሄደ ይገኛል። የበሬዎች ግዢ ከመካሄዱም በፊት ሆነ በእርድ ወቅት የሃኪሞች ክትትልና ምርመራ እንደማይለይ ተናግረው ነግራቹን ብትመጡ ኖሮ ጊቢው ከሚያረባቸው ላሞች ከወተቱም እንዲሁም ከንቁላሉ አስፈላጊ ከሆንም ጠብሰን እንጠብቃቹ ነበር" ብለው ንግግራቸውን አሳርገዋል።

ከ Dr. Hika ከተለያየን ቡሃላም ከፋሲሊቲ ሃላፊ ከሆኑት Dr. ቀጄላ ጋር ያለውን ሙሉ ሂደት በቃላት ካወራንና እኛ ጋር የነበሩትን ጥያቄዎችንም ካነሳን ቡሃላ በአካል ቄራውን መጎብኘት ችለናል። ባየነውም ነገር ምንም ጥርጣሬዎችን ሚፈጥሩ ነገራቶችን ባለመመልከታችን ጊቢውን አመስግነን ከተማሪዎች የቀረቡልንን ጥያቄዎችና ምክረሃሳቦች ሙሉ በሆነ ግልፀኝነት አንስተን ተለያይተናል። ለወደፊትም ማንኛውም ጥርጣሪ ሚፈጥሩ ነገራቶች  ካሉ በማንኛውም ሰአት በተወካዮች በኩል መጥቶ መመካከርና ምክረ ሃሳቦችን መቅረብ እንደሚቻል Dr. ቀጄላ የማሳረጊያ መልክታቸውን አስተላልፈው የመጡትን የተማሪ ተወካዮች በክብር ደስ ከሚል አቀባበል ጋር ሸኝተዋል።

ተማሪዎቻችንም በፊት ሲያደርጉት እንደነበረው ሁላ ያለምንም ጥርጣሬና አለመረበሽ የሚቀርብላቸውን "there 4" እንዲያጣጥሙ ለማስታወስ ወደድን።

©️AAU6kilojemea

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Dec, 06:30


አንተ ባለደካማ መንፈስ ሆይ፣
የት ነህ? ይህ (የኢስላም) መንገድ አደም የደከመበት፣ ኑሕ ያለቀሰበት፣ ኢብራሂም ወደ እሳት የተወረወረበት፣ ኢስማዒል ለመታረድ የቀረበበት፣ ዩሱፍ በርካሽ ዋጋ ተሽጦ ለብዙ ዓመታት በእስር ቤት የቆየበት፣ ዘከሪያ በመጋዝ የተገዘገዘበት፣ ድንግልና ከደጋጎቹ ነቢያት የሆነው ያህያ የታረደበት፣ አዩብ መከራን የቀመሰበት፣ ዳዉድ ሊሸከመው ከሚችለው በላይ ያለቀሰበት፣ ኢሳ ከአውሬዎች ጋር በጫካ የሄደበት፣ ነብያችን ሙሐመድም ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ድህነትንና ሁሉንም ዓይነት ችግር የቀመሱበት መንገድ ሆኖ ሳለ አንተ በመዝናኛ እና በጨዋታ ትኖራለህን?

- ኢብኑል ቁዪም

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Dec, 18:10


📢 Qawa’id Series!: Session 1 

The 5 Kilo Campus Muslim Students Jemeah is excited to launch the Qawa’id Series – a bi-weekly dawrah program designed to share timeless Islamic knowledge. Each session will focus on a short poem (manzumat) selected to provide essential guidance on various aspects of Islamic teachings. Dinner will be provided after every session, making it a complete experience of learning and community bonding. 


Chosen Poem for Session 1:
🌟 Manzumat Ahsanul Akhlaq 🌟 
🖋 Authored by Sheikh ‘Amir Bahjat

The poem offers profound insights into the principles of Islamic ethics beginning with ethics with Allah to ethics with the parents and finally the wider public sphere. It beautifully highlights the noble character traits every Muslim should strive to embody in daily life. 

Session Details
📅 Date: Friday, December 27, 2024 
🕒 Time: From ‘Asr (4:00 PM) to Isha’ (8:00 PM) 
📍 Venue: Al-Aqsa Mosque, 6 Kilo 
🎙 Instructor: Ustaz Abduselam Reshid


Why Attend?
- Strengthen your aqeedah knowledge through precise lessons
- 🌿 Gain a deeper understanding of Islamic ethics and how they shape our lives. 
- 📚 Learn through engaging reflections and explanations from Ustaz Abduselam Reshid. 
- 🌍 Build connections with fellow students in a spiritually enriching environment. 
- 🍴 Enjoy a wholesome dinner and foster a sense of community.

🔗 Register Now: https://forms.gle/Hm8wnReJaG3xqsX27

📢 Invite your friends and classmates to join this transformative journey of learning and growth.

#QawaidSeries #IslamicEthics #CommunityLearning #AhsanulAkhlaq #SpiritualGrowth

©fivekjemaa

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Dec, 09:07


አሏህን እንፍራ! አሏህን እንፍራ! እሏህን እንፍራ!

ምስጋና ለአለማቱ ጌታ ለሆነው አላህ የተገባ ይሁን። የአላህ እዝነትና ሰላም ለአለማት እዝነት በተላኩት ነብዩ ሙሐመድ ﷺ፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለባልደረቦቻቸው እና የእርሳቸውን ፈለግ በተከተሉት ላይ ይሁን።

ኢስላም ሰፊና ጥልቅ አስተምህሮቶች፤ ረቂቅና ጥልቅ መመሪያዎችና ድንጋጌዎች አሉት። ሁሉንም የህይወት ዘርፎች ዳሷል። ሳያስተምረን ያለፈው የህይወት ጉዳይ የለም። በተለያየ መልክና ዘዴ እያንዳንዱን የህይወት ክፍል በመዳሰስም ወደር የሌለው ሃይማኖት መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ይህንንም እውነታ የማንኛውም አማኝ ልቦናና ህሊና ያውቀዋል።

በዛሬው እለት በግቢያችን ብሎም በካምፓሳችን GC Birthday የሚል የጥፋት ክብረ በዓል እንደተዘጋጀ እየሰማን ነው። ምንም እንኳን እንደዚህ ዓይነት ዝግጅቶች ከላይ ሲታዩ ምንም ጉዳት የሌላቸው ቢመስሉም ነገር ግን እንደ ሙስሊምነታችን ግን ይህንን እና መሰል ዝግጅቶችን በቁርኣንና በሱና መነፅር መገምገም ግዴታችን ነው። በዚህም አጭር ጽሑፍ ለምን ከዚህና ተመሳሳይ ዝግጅቶች መራቅ እንዳለብን ለማየት እንሞክራለን።

1. በእንደዚህ አይነት ዝግጅቶች በጣም አሳሳቢ ከሆኑ ጉዳዮች አንዱ በወንዶች እና በሴቶች መካከል ተገቢ ያልሆነ መቀላቀልን መፍጠሩ ነው። አላህ ምዕመናንን እንዲህ በማለት አዟል-

"ለምእመናን ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን (ያልተፈቀደን ከማየት) ይከልክሉ፤ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፤ ይህ ለነሱ የተሻለ ነው፤ አላህ በሚሠሩት ሁሉ ውስጥ ዐዋቂ ነው፡፡ ለምእምናትም ንገራቸው፡- ዓይኖቻቸውን ይከልክሉ፡፡ ብልቶቻቸውንም ይጠብቁ፡፡ ..." (ሱረቱ-ኑር 30 - 31)

ነብዩ ሙሐመድም ﷺ እንዲህ ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡- “ማንም ወንድ ከሴት ጋር ብቻውን አይሆንም ነገር ግን ሦስተኛቸው ሰይጣን ቢሆን እንጂ" (ሱነኑ ቲርሚዚይ)

በአሁን ዘመን በሴቶች እና ወንዶች መካከል መቀላቀል በሸሪዓ የታዘዘ እስኪመስል ድረስ ተለምዷል፤ ከዚህ ነገር የሚያስጠነቅቅ አካልም እንደ አክራሪ እና አጥባቂ ተደርጎ ይታያል፤ ጭራሽ ከቅልቅልም አልፎ ወንዶች ሴቶችን መጨበጥ፣ ማቀፍ ወዘተ እንደተራ ነገር ነው የሚቆጠረው፤ ከዚህ ፈተና አሏህ የጠበቃቸው ወንድምና እህቶች እንደ ኃላቀር እና ያልሰለጠነ እየተቆጠሩ ነው!

ኢስላም ወንድ እና ሴት ምዕመናን ዓይኖቻቸውን ከሐራም እንዲከለክሉ አዟል፤ አንድ ወንድ ዘመድ ያልሆነችን ሴት ከአንድ ጊዜ በላይ እንዳያይ ከልክሏል፤ አንዷም ጊዜ ብትሆን በአጋጣሚ እንጂ ታስቦበት የተደረገ መሆን የለበትም! አስፈላጊ ከሆነ ነገር ውጪ ወንዶችና ሴቶች በቀጥታ እንዳይነጋገሩ ገደብ አስቀምጧል፤ ከዚያም አልፎ እጅግ አስገዳጅ ሁኔታ ካልተፈጠረ በስተቀርም ወንዶችና ሴቶች በአንድ ቦታ ያለምንም ግርዶሽ እንዳይሰባሰቡ ከልክሏል። ይህ ሁሉ ክልከላም በወጣት ወንዶች እና ሴቶች መካከል ሲሆን የበለጠ የጠበቀ ይሆናል!

የኛ ሁኔታ ግን ሴት እና ወንድ አንድ ላይ እንዲሰበሰቡ የታዘዝን ይመስል ካልተሰባሰብን እያልን ነው።
"የወጣት ሴት ድምጽ ዓውራ ነው" ያሉ ዑለሞች የሌሉ እስኪመስል ድረስ ወንዶችና ሴቶች እርስ በርስ መሳሳቅ እና መጫወትን ልማዳችን አድርገንዋል። "ሴት ልጅ ለግዴታ ጉዳይ ካሆነ በስተቀር ከቤቷ አትውጣ፤ ከወጣችም ተቆነጃጅታ አትውጣ" የሚል ነብያዊ ትዕዛዝ የሌለ እስኪመስል ድረስ ሴቶቻችን ራሳቸውን አስውበውና ተጋጊጠው ሲወጡ እያየን ነው። "አንዳችሁ ለርሱ ያልተፈቀደችን ሴት ከሚጨብጥ ጭንቅላቱ በሚስማር ቢበሳ ይሻለዋል" የሚል ነብያዊ ሐዲስ የሌለ እስኪመስል ድረስ ወንዶችና ሴቶች ካልተቃቀፍን እያለን ነው።

አላህን እንፍራ ያ ኡመተ ሙሐመድ!

2. ከሁለቱ የምስክርነት ቃሎች በመቀጠል ሁለተኛው የእስልምና መሰረት የሆነውን ሰላትን በህመም ይሁን ጦርነት ውስጥ ሆነን እንድንሰግድ አላህ ግዴታ አድርጎብናል። በሰውየው እና በኢስላም መካከልም ያለው ገመድ ሰላት መሆኑን ነብያችን አስተምረውናል። ሰላትን የተወ ሰው ከኢስላም ምንም ድርሻ እንደሌለው በግልጽ አስረድተውናል። በዚህ የጥፋት ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ ያሰባችሁ ወንድሞችና እህቶች የሚከተለው የአሏህ ዛቻ በእናንተ ላይ እንዳይሆኑ ፍሩ!

"ከእነሱም በኋላ ሶላትን ያጓደሉ (የተዉ) ፍላጎቶችንም የተከተሉ መጥፎ ምትኮች ተተኩ! የገሀነምንም ሸለቆ በእርግጥ ያገኛሉ፡፡" (መርየም 59)

ይህቺን አንቀፅ ሲያብራሩ ዑመር ኢብኑ አብዱል አዚዝ እንዲህ ይላሉ- “ሶላታቸውን ተዉ ማለት ምንም አይሰግዱም ማለት ሳይሆን በሰዓቱ መስገድን ትተዋል ማለት ነው። (ተፍሲር ኢብን ከሲር)


ነብዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- "ባሪያው በፍርድ ቀን የሚጠየቅበት የመጀመሪያው ጉዳይ ሶላት ነው።"

ወንድሜ ሆይ፤ እህቴ ሆይ፤
የውመል ቂያማ አላህ ፊት ቁመህ ስለዛሬው ጁምዓ ሰላት ሲጠይቅህ GC Birthday እያከበርኩ ነበር ብለህ ልትመልስ ነውን? ልትመልሽ ነውን? ስለዛሬዋ አስር፤ መጝሪብና ዒሻእ ስትጠየቅስ ምን ብለህ ልትመልስ ነው?

አላህን በማመጽ ምንም የሚገኝ ኸይር የለም፤ የአላህን ትዕዛዝ በመከተልም የሚታጣ ምንም ኸይር የለም፤ ለአላህ ብሎ አንድን ነገር የተወ ሰው አላህ ለርሱ የተሻለን ይሰጠዋል

"በእኛ እና በነርሱ (በከሃዲያን) መካከል ያለው መለያ ሶላት ነው፤ ሰላትን የተወ ሰው በእርግጥ ክዷል!" (ነብዩ ﷺ)

በሰላት ጉዳይ አላህን እንፍራ!

3. ሙዚቃ እና ዘፈን ልብን አላህን ከማውሳት የሚያዘናጉ በመሆናቸው በእስልምና በግልፅ ተከልክለዋል። ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- “ከእኔ ኡመት ውስጥ ዝሙትን፣ ሐርን፤ አስካሪ መጠጥን እና ሙዚቃን ልክ እንደሐላል የሚይዙ ይመጣሉ”

ሙዚቃ ከባቢን በሚቆጣጠርባቸው ዝግጅቶች ላይ መገኘት ይህንን የነብዩን ንግግር በቀጥታ መቃረን ነው። ዘፈን የባሪያን ልብ ያደርቃል፤ በቁርዓን እርካታ እንዳያገኝ ያደርገዋል፤ አሏህን እና ቂያማን ከማስታወስ ያዘናጋዋል፤ በዚህ ምድር የመጣበትን ዓላማ እንዲረሳ ያደርገዋል፤ ሌሎች ወንጀሎችንም በባሪያው ፊት ቀላል ያደርግለታል።

ታላቁ ሰሓቢይ አብዱሏህ ኡብኑ መስዑድ ስለዘፈን እና መዘዞቹ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦ “ዘፈን የዝሙት ማጪያ ነው፡፡

ኢብኑ ቀዪምም እንዲሁ ስለዘፈን ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ፦ "ዘፈን እና ቁርዓን በአንድ ባሪያ ልብ ውስጥ አይሰበሰቡም አንዱ ሌላኛው ያሸነፈው ቢሆን እንጂ"

ከዚህ ሁሉም በተጨማሪ ዘፈን በዚህ ህዝብ ላይ ለሚደርሱ ችግሮች መንስኤ ሊሆን እንደሚችል ነብዩ ﷺ እንደዚህ በማለት አብራርተዋል፦ “በዚህ ህዝብ ላይ ምድር ተከፍታ መስመጥ፣ የመልክ መቀየርና በድንጋይ መቀጥቀጥ ይከሰታል” ሲሉ ከሙስሊሞች አንዱ “መቼ ነው?” ብሎ ሲጠይቅ መልዕክተኛውም “ዘፋኝ ሴቶችና ሙዚቃ ይፋ ሲወጡ እንዲሁም አስካሪ መጠጥ በግልፅ የተጠጣ ጊዜ ነው፡፡” በማለት መለሱለት፡፡

አሁን እያየን ያለነው ይህንን አይደለምን? ሙስሊሞች ዘፈን ማዳመጥ ከቁርዓን በላይ አጅር ያስገኛል የተባልን ይመስል የዘፈን ሱሰኛ አልሆንምን?

ወንድሜ ሆይ፤ እህቴ ሆይ፤ እስኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፡
በቀን ለምን ያክል ጊዜ ቁርዓን ታዳምጣለህ? ታዳምጫለሽ? ለምን ያክልስ ጊዜ ትቀራለህ? ትቀሪያለሽ? እስኪ ከዚያን ከዘፈንስ ጋር እንዴት እንደሆን ራስህን መርምር? ራስሽን መርምሪ?

ታላቁ ታቢዒይ ራፊዕ ኢብኑ ሐፍስ አል-መደኒ፦ “አራት አይነት ሰዎችን አላህ የትንሳኤ ዕለት በእዝነት አይን አይመለከታቸውም። ደጋሚ፣ አስለቃሽ፣ ዘፋኝ እና ባሏን ያታለለች" ማለታቸውን ኢብኑ አቢዱንያ ዘግበዋል፡፡

AAU - Muslim Students Union

20 Dec, 09:07


ወንድሞች እና እህቶች፤ ከነዚህ አራት ሰዎች መሆን እንፈልጋለን? የውመል ቂያም አላህ ፊት ከደጋሚ እኩል መታየትን ነው የምንሻውን?

ወንድሞች አላህን ፍሩ! እህቶች አላህን ፍሩ! አላህን እንፍራ!

4. ኢስላም ወንዶችም ሆኑ ሴቶች ምን ዓይነት አለባበስ መከተል እንዳለባቸው በግልጽ ደንግጓል። ሴቶች ከሰውነታቸው የቅርብ ዘመድ ላልሆኑ ሰዎች የትኛውንም የሰውነታቸውን ክፍል እንዳያሳዩ ተከልክለዋል። የሰውነታቸውን ቅርጽ የሚያሳይና ጾታዊ ፍላጎትን የሚቀሰቅስን ልብስ እንዳይለብሱ በግልጽ ተከልክሏል። ከዚያም አልፎ የሌሎችን ትኩረት ለመሳብ በማሰብ ከቤታቸው ውጪ ሽቶ እንዳይቀቡ ተከልክለዋል። ይህንንም ያደረገች ሴት እንደ ዝሙተኛ እንደምትቆጠር ነብዩ ﷺ በግልጽ ተናግረዋል።

ወንዶች አስገዳጅ ሁኔታ ካልኖረ በስተቀር ከሴቶች ጋር በቀጥታ ፊት ለፊት እንዳይነጋገሩ ተከልክለዋል። የዚህ ዑማ ምርጦች የተባሉት ሰሓቦች እንኳን ከዚህ ዑማ ሴቶች ሁሉ በላጭ የሆኑትን የነብዩን ባለቤቶች ዕቃ በሚጠይቁበት ጊዜ እንኳን ከመጋረጃ ኃላ ሆነው እንዲጠይቁ ታዘዋል። አላህ እንዲህ ይላል፦
"ዕቃንም (ለመዋስ) በጠየቃችኋቸው ጊዜ ከመጋረጃ ኋላ ኾናችሁ ጠይቋቸው፡፡ ይህ ለልቦቻችሁ፤ ለልቦቻቸውም የበለጠ ንጽሕና ነው፡፡ " (አህዛብ 53)

ይህ ለነዚያ ምርጥ ትውልዶች የተባለ ከሆነ ለኛስ ምን ሊባል ነው?

ወንድሜ ሆይ፤
የዚህ ዑማ ምርጥ የሆኑት የነብዩ ባልደረቦች እንኳን እቃ ከመጋረጃ ጀርባ ጠይቁ እየተባሉ ያንተ ከሴቶች ጋር ተቀላቅለህ ፊት ለፊት መሳሳቅ ምን ይባላል? "ይህ ለልቦቻችሁ፤ ለልቦቻቸውም የበለጠ ንጽሕና ነው፡፡" የተባለው ላንተ አይሰራምን? ወይስ ያንተ ልብ ከሰሓቦች እና ከነብዩ ባለቤቶች በላይ ንጹህ ነው? እህትህ ከሌላ ወንድ ጋር እንድታደርገው የማትፈልገውን ነገር ለምንድነው ከሌላ ወንድ እህት ጋር የምታደርገው? አላህን አትፈራምን?

እህቴ ሆይ፤
የዚህ ዑማ ሴቶች ሁሉ ምርጥ የሆኑት የነብዩ ባለቤቶች እንኳን የዚህ ዑማ ምርጦች ከሆኑት የነብዩ ባልደረቦች ጋር በቀጥታ መነጋገር ተከልክለው ያንቺ ከወንዶች ጋር ተቀላቅለሽ መሳሳቅ ምን ይባላል? ይህ ለልቦቻችሁ፤ ለልቦቻቸውም የበለጠ ንጽሕና ነው፡፡" የተባለው ላንቺ አይሰራምን? ወይስ ያንቺ ልብ ከሰሓቦች እና ከነብዩ ባለቤቶች በላይ ንጹህ ነው? "በቤቶቻችሁም ውስጥ እርጉ፡፡ እንደ ፊተኛይቱ መሃይምነት ጊዜ መገለጥም በማጌጥ አትገለጡ፡፡" የሚለው የጌታሽ ንግግር አንችን አይመለክትንምን?

ለነዚህ ጥያቄዎች መልስ አለን? አሏህ የውመል ቂያማ ሲጠይቀን የምንመልሰው ነገር አለን?

በመጨረሻም! ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣
የምንኖረው እምነታችንን አጥብቆ መያዝ ልክ ፍም እንደመጨበት በሚከብደብት ጊዜ ላይ ነው። እምነቱን ጸንቶ የሚይዝ ሰው እንደባይተዋር የሚቆጠርበት ዘመን ላይ ነን። ይህም ልክ ነብዩ ሙሐመድ ﷺ፡- “እስልምና እንግዳ ነገር ሆኖ ነው የጀመረው፤ እንደጀመረው ወደ እንግዳነት ይመለሳል ፤ስለዚህ ለእንግዶች ብስራት ይገባቸው።" ብለው እንደተናገሩት ነው።

ወንድሞቼ እና እህቶቼ፣ የምንወስዳቸው እርምጃዎች ሁሉ ለእምነታችን ያለንን እንደሚያንጸባርቁ አስታውሱ። ጊዜያዊ ደስታን ለማግኘት ኢስላማዊ እሴቶችን በሚቃረኑ ዝግጅቶች ላይ መሳተፍ ከአላህ ጋር ያለንን ግንኙነት አደጋ ላይ መጣል እንጂ ሌላ ምንም ዋጋ የለውም። ወደ እርሱ ውዴታ የሚወስዱ መንገዶች በመምረጥ ልባችንን፣ ዲናችንን እና ክብራችንን እንጠብቅ፤ አላህም የተሻለ ነገርን ይሰጠናል።

ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- "ለአላህ ብሎ አንድን ነገር የተወ አላህ በተሻለ ይተካዋል።"። ከሐራም ተግባራት መራቅን በምንመርጥበት ጊዜ አላህ በዱንያም በአኺራም የላቀ ነገር ይሰጠናል። ተማሪዎች እንደመሆናችን መጠን ለአቻዎቻችን እና ጓደኞቻችን የእስልምና አምባሳደሮችና አርአያ ነን። ኢስላማዊ እሴቶችን በሚቃረኑ ዝግጅቶች ውስጥ መሳተፍ ይህንን ማንነት የሚንድ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፡- "እናንተ ለሰው ልጆች ከተፈጠሩት ሕዝቦች ሁሉ በላጭ ናችሁ። በመልካም ነገር ታዛላችሁ ከመጥፎም ነገር ትከለክላላችሁ በአላህም ታምናላችሁ።" ራሳችንን እንዲህ በማለት እንጠይቅ እስኪ፡ "እኔ እንደዚህ ባሉ ዝግጅቶች ላይ በመገኘት ይህን የተከበረ ሀላፊነት እደግፋለሁኝ? ወይስ መገኘቴ የታዘዝኩትን በጥሩ ማዘዝንና ከመጥፎ መከልከልን እንዳልወጣ ያደርግኛል? ለአላህ ሲጠይቀኝ የምመልስለት ነገር አለን?"

አላህ ዲናችንን አጥብቀን እንድንይዝ ያድርገን፣ እሱ ወደወደደው ነገር ይምራን፣ ወደ ጥፋትም ከሚወስዱን ተግባራት ይጠብቀን። አሚንን!!!!

©️fivekjemaa

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Dec, 03:11


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

18 Dec, 12:33


በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ከሶላት ጋር በተያያዘ ከተማሪዎች አገልግሎት እና ከዩኒቨርሲቲው የደህንነት ክፍል ሀላፊዎች ጋር ያደረጉት ውይይት ተጠናቋል:: በውይይቱ ሙስሊም ተማሪዎች "ወይ ከግቢ ወጥተን እንድንሰግድ የግቢውን በራፍ ክፈቱልን ካልሆነ ደግሞ እዚሁ ከግቢው ውስጥ እንድንሰግድ ቦታ አመቻቹልን::" ብለው የጠየቁ ቢሆንም የዩኒቨርሲቲው አመራሮች "በግቢ ውስጥ ለየብቻም ሆነ በቡድን መስገድ አትችሉም:: ከአሁን ቡሃላ ለመስገድ የሚያስብ አካል ካለ ሙሉ ሀላፊነቱን ራሱ ይወስዳል::" በማለት ምላሽ ሰጥተዋል::

ፍትሕ ያሻል!

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

18 Dec, 10:09


የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በግቢው ውስጥ ሶላት መስገድን ከለከለ!

  በትላንትናው እለት በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ሶላት ሲሰግዱ የተገኙ 7 ተማሪዎች ተይዘው ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው ሲሆን ተማሪዎቹም "ወይ እንድንሰግድ ከ12 ሰዓት ቡሃላ በር ክፈቱልን ወይ ደግሞ እዚሁ እንድንሰግድ ፍቀዱልን::" የሚል ጥያቄ አቅርበዋል:: (ዩኒቨርሲቲው ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ የግቢውን በር ስለሚዘጋ ተማሪዎች ለመግሪብ እና ዒሻ ሶላት መውጣት አይችሉም::)

  በዛሬው እለትም በዚህ ሰዓት (ከቀኑ 6:50) ሁሉም ሙስሊም ተማሪ ከተማሪዎች አገልግሎት ቢሮ በመገኘት ጥያቄያቸውን እያቀረቡ መልስም እየጠየቁ እና እየተወያዩ ይገኛሉ::

አላህ ያግዛቸው ዘንድ ዱዓችን ነው!

©EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

17 Dec, 10:50


የዲላ ዩኒቨርሲቲ በተቋሙ ውስጥ ኒቃብ ለብሶ መግባትንም ሆነ መንቀሳቀስ ከለከለ!

   የዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች አገልግሎት ሀላፊ እና የደህንነት ክፍል ሀላፊ በዛሬው እለት የሙስሊም ተማሪዎችን ተወካዮች ጠርተው እንደገለፁት ባለፉት ሶስት አመታት ሙስሊም ተማሪዎች በነፃነት ሲለብሱት የነበረውን ኒቃብ ከአሁን ቡሃላ ለብሳችሁ መግባትም ሆነ መንቀሳቀስ አትችሉም ሲል አሳውቋል:: እንደ ምክንያትም ኒቃብ የሴት ልጅን ፊት ስለሚሸፍን የደህንነት ስጋት ይሆናል በማለት ገልፀዋል::

  ተማሪዎቹ ኒቃብ እሴታቸው እና እምነታቸው መሆኑን ገልፀው ሊከለከልበት የሚችል ብሎም የደህንነት ስጋት የሚሆንበት አውድ እንደሌለ ቢያስረዱም ሰሚ እንዳላገኙ አሳውቀዋል::

••• ተጨማሪ መረጃዎችን እና የተማሪዎቹን እንቅስቃሴ የምናሳውቅ ይሆናል::

©️EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Dec, 07:53


“ይህ ድርጅት ተቋቁሞ በብዙ ውጣ ውረዶች ውስጥ አልፎ እዚህ ደርሷል እስካሁን 60 (ስልሳ) መሻይኾችን አስመርቆ በአሁኑ ሰዓት 150 (አንድ መቶ ሃምሳ ተማሪዎቸን) ተቀብሎ በማስተማር ላይ ይገኛል። የተቋሙን ራዕይ እና ተልኮ ለማሳካት በሚደረግ የእውቀት ቅብብሎሽ ሂደት ውስጥ ሁሉም በየዘርፉ ድርሻውን አውቆ በመውሰድ የሚጠበቅበትን ሊወጣ ይገባል። በዚህም ሂደት ውስጥ የቅብብሉ ሂደት ስር የሰደደ እና ዘመናትን የሚሻገር እንዲሆን የሚሰሩ ስራዎች ባጠቃላይ ግለሰቦች ላይ ያተኮሩ ሳይሆን ተቋማት ግንባታ ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆን አለባቸው። ሰዎች ይደክማቸዋል ወይም ቀናቸው ሲደርስ ወደ አላሀ (ሱ.ወ) ይጠራሉ። ከተቋማት በላይ ሰዎችን የምናገዝፍ ሲሆን እነዚህ ሰዎች ሲደክሙ ወይም ወደ አላህ ጥሪ ሲደርሳቸው ተቋማቱ ይደክማሉ ብሎም ይዘጋሉ። እስካሁን በሄድንበት መንገድ ቀጣይነት ያለው እና በአንድ ሰው መኖር ላይ ህልውናው ያልተንጠለጠለ ተቋም ለመመስረት በማይመች ጎዳና ላይም ቢሆን ተጉዘን ለመገንባት ሙከራዎችን በማድረግ የተለያዩ የህብረተሰባችንን ክፍሎች በመጋበዝ ከተቋሙ የድርሻቸውን እንዲውስዱ እያደረግን እንገኛለን። ውድ ተማሪዎች እናንተም የምታበረክቱትን አስተዋጻኦ ሳታሳንሱ በዚህ ተቋም ውስጥ ያላችሁን ድርሻ ውሰዱ። የተቋም ግንባታው ባቡር ከ ሰባት ዓመት በፊት መንቀሳቀሱን ጀምሯል፤ አልሃምዱሊላህ እስካሁን አልቆመም ወደፊትም አይቆምም። ባቡሩ ማንንም ለመጠበቅ አይቆምም ኑ ተቀላቀሉን አብረን ወደ ግባችን እንሂድ።”

- ሸይኽ ሙሐመድ ሓሚዲን በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለስድስት ኪሎ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች የሰጡት ምክር

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Dec, 07:38


"ሰላቢዎች ሁሉ ወዮወላቸው፤ ለእነዚያ ከሰዎች ለመግዛት ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፤ እነርሱም (ለሰዎች) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎሉ (ለሆኑት)።" (አል-ሙጠፊፊን 1-3)

አል-መሀይሚ ምዕራፉ ለምን በዚህ ስም እንደተሰየመ ሲያብራሩ እንዲህ ብለዋል፡-
"በዚህ ስያሜ የተሰየመው የፍጥረትን ትልቁን መብት ያጓደለ ሰው ከአላህ ዘንድ ታላቅ ወዮታ እንደሚገባው ለመጠቆም ነው፡ ስለዚህ የአላህን ትልቁ መብት የሆነውን በእርሱ፣ በአንቀጹ እና በመልዕክተኞቹ የማመንን መብት በቸልታ የተወ ሰው እንዴት ይሆን ይሁን?"

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Dec, 18:52


🌟 Coming Soon: Qawa’id Series! 🌟

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 👋

We are excited to announce the launch of the Qawa’id Series – a bi-weekly program designed to explore timeless Islamic principles through classical poetry and meaningful discussions.

🕌 What to Expect:
- Short, powerful lessons based on classical Islamic texts (manzumat)
- Open to all levels – everyone is welcome to join!
- An opportunity to strengthen your faith, character, and understanding of Islam.
- Held every two weeks on Friday afternoons at Al-Aqsa Masjid
- Warm meal for dinner as we learn and grow together

Stay tuned for the full schedule

📢 Spread the Word and Get Ready to Join Us!

#fivekjemaa #QawaidSeries #IslamicLearning #TimelessWisdom #CommunityGrowth

©️fivekjemaa

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Dec, 18:36


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች ሱና ፋውንዴሽንን ጎበኙ።
***
ትላንት ማለትም ታህሳስ 5 ቀን 2017 ዓል የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ሙስሊም ተማሪዎች በአሚሮቻቸቸው መሪነት በህብረት ወደ ሱና ፋውንዴሽን በመምጣት ፋውንዴሽኑን እና በስሩ የሚገኙትን ክፍሎች መጎብኝት ችለዋል። ተማሪዎቹ ወደ ተቋሙ ሲመጡ በፋውንዴሽኝኑ አስተዳደር እና ሰራተኞች ሞቅ ያለ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን፤ ይህን ተከትሎ የፋውንዴሽኑ ማኔጂንግ ዳይሬክተር የሆኑት ኑሩ ሙሃመድ (ዶ/ር) ተማሪዎቹን እንኳን ወደ ተቋማችሁ በደህና መጣችሁ በማለት ከተቀበሏቸው በኋላ አጠቃላይ ስለ ፋውንዴሽኑ እና በውስጡ አቅፎ ስለያዛቸው ተቋማት(ስለ ሱና ወቅፍ እና ሃበት ማሰባሰብ ዳይሬክቶሬት፤ ሱና ዩኒቨርሲቲ፤ እና ዳዕዋ ቲቪ) ዓላማ፤ አመሰራረት፤ ያሉበት ሁኔታ እና የወደፊት እቅድ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋቸዋል።

በማስቀጠልም ዳይሬክተሩ ተማሪዎቹ ለግላቸው፤ ለማህበረሰባቸው፤ በሎም ለሃገራቸው ሁለንተናዊ እድገት እና እቅድ መሳካት ያላቸውን ሚና አሳንሰው በማየት ዛሬያቸውን አባክነው ነገ ላይ እንዳይቆጩ ጠንክረው እንዲማሩ ምክር አዘል መልዕክታቸውን አቀብለዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሱና ዩኒቨርሲቲ የ ሬጅስትራር እና የተማሪዎች ቅበላ ሃላፊ የሆኑት ሸይኽ ሙሃመድ ሃሰን ተማሪዎቹ ሳይዘናጉ ሃይማኖታቸውንም የ አካዳሚያዊ ትምህርቱንም ጎን ለጎን ማስኬድ እንዳለባችው እውቀታቸውን ከዩኒቨርሲቲ ልምዳቸው ጋር ቀምረው ምክራቸውን ለተማሪዎቹ ለግሰዋል።

ተማሪዎቹም ባዩትም ሆነ በሰሙት ነገር ደስተኛ በመሆን ወደፊት በብዙ መልኩ ተቋሙን መጥቀም እና ከተቋሙ መጠቅም የሚያስችሉ ንድፈሳሃሳቦችን ይዘው ወደ ተቋሙ በመመለስ ከተቋሙ ጋር አብረው እንደሚሰሩ ገልጽዋል።

በመጨረሻም ተማሪዎቹ የድርጅቱን ፋሲሊቲዎች በመጎብኝት እና የፋውንዴሽኑን ዋና ስራ አስፈጻሚ ተወዳጁን ሸይኽ ዶ/ር ሙሃምድ ሃሚዲንን ያገኟቸው ሲሆን ከሳቸውም ጥቂት ምክሮችን በመቀበል የእለቱን መርሃግብራቸውን አገባደው ወደግቢያቸው ተመልሰዋል።

©ዳዕዋ ቲቪ

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

07 Dec, 15:58


የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ጋር ተወያየ!

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ትኩረቱን በሙስሊም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሁለንተናዊ ችግር እና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ አድርጎ የሚሰራው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በመጅሊስ በኩል ከተቋቋመው የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ከፍተኛ አመራሮች ጋር ሰፊ ውይይት አድርጎል:: በውይይቱ የተለያዩ ነጥቦች የተነሱ ሲሆን በዋናነትም ከሙስሊም ተማሪዎች የመብት ትግል እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮች በጥልቅት ተጠቅሷል::

   በአላህ ፈቃድ ተማሪዎቻችንን አቅፈን ከሙስሊም ተቋማት ጋር በመተባበር በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ዙሪያ እየደረሱ ያሉ መግፋቶችንና በደሎችን የምንፈታ ይሆናል::

  አላህ መልካም ለውጦችን ከሚያመጡት ያድርገን!

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

06 Dec, 05:32


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

03 Dec, 14:46


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከነሲሓ አካዳሚ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተከታታይ የሸሪዓ ትምህርትን የተመዘገባችሁ በሙሉ በኢሜላችሁ የግሩፕ ሊንክ የገባላችሁ በመሆኑ በተላከላችሁ ሊንክ በመጠቀም ግሩፑን ጆይን አድርጉ!

ኢሜይሉን inbox ላይ ካላገኛችሁት spam folder ላይ ቼክ አድርጉት።

ተመዝግቦ ኢሜይል ያልገባለት በ @Aaumuslimstudentsunion1 አናግሩን።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

03 Dec, 12:07


Gamtaan Barattoota Musliimaa Dhaabbilee Barnoota Olaanoo Itiyoophiyaa(University) Yaa'ii Waliigalaa isaa gaggeesse!

•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

Waldaan Barattoota Musliimaa Dhaabbilee Barnoota Olaanoo Itiyoophiyaa waggoota 3f rakkoo waloo barattoota muslimaa yunivarsiitiiwwan keessa jiran furuuf waliin hojjachaa ture. Adoolessa 20/2017 hanga Adoolessa 22/2017tti Finfinnetti walga’ii waliigalaa gaggeessee jira. Gamtichi  Majlisa Federaalaa irraa beekkamti kan argate yoo ta'u walga'icha irratti  Hojiiwwan waggoota 3n darban keessatti hojjetaman gamaaggamuun kallattii gara fuula duraa kaa’uun yaa’ii waliigalaa kana keessatti keessumattuu qabsoo mirgaa waliin walqabatee waraqaawwan qorannoo adda addaa dhiyaataniiru, kallattiin furmaataas kaa’ameera.

Dhumarratti konfiraansichi hoggantoota adda addaa gamtichaa filachuun xumuramee jira.

🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀🍀

Gamtaa Barattoota Musliimaa
Dhaabbilee Barnoota Olaanoo Itiyoophiyaa !!!!


https://t.me/EHEMSU

AAU - Muslim Students Union

02 Dec, 11:36


Jama'aa Barattoota Muslimaa 6 Kiilootiin kan qophaa'u wal-dorgommiin gaaffiif deebii addaa Qalam badhaasoota hawwachiisoo waliin marsaa lammaffaatiin deebi'ee jira!

Dorgommiicharratti:
⭐️ Namoota dorgommii torban torbaniin taasifamu injifataniif badhaasa kaardii moobaayilaa
🌟 Warra ji'a ji'aan sadarkaa dursaa irratti xumuraniif badhaasa kitaabaa akkasumas
🏆Dorgommii waliigalaa irratti warra 1-3 bahaniif badhaasni maallaqaa guddaa qophaa'e jira.

🏵Kana malees hirmaattota dorgommii kanaa hundaaf waraqaan ragaa ni kennama!

Dorgommii kana irratti hirmaachuuf liinkii armaan gadii fayyadamuun galmaa'aa
👇👇👇
https://forms.gle/gqVoNDphT3ekdAEk6

NB:
📍Dorgommiin kun muslimoota hundaaf banaadha. Barattoonni kaampaasiiwwan Yuunivarsiitii Finfinnee hundarraa, yuunivarsiitiiwwan kan biraa irraa, akkasumas alarraa barattoota kan ta'anis kan hin taanes hirmaachuu ni danda’u.
📍Dorgommiin kun karaa onlaayina(online) chaanaalii jama'aa 6 kiiloo irratti gaggeeffama.

©️ 6 Kilo Jemea

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

02 Dec, 11:35


በ6 ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የሚዘጋጀው ቀለም ልዩ የጥያቄና መልስ ውድድር ከአጓጊ ሽልማቶች ጋር በሁለተኛ ዙር ተመልሷል!

በውድድሩ:
⭐️ለሳምንታዊ ውድድር አሸናፊዎች የሞባይል ካርድ ሽልማት
🌟ወሩን በመሪነት ደረጃ ላይ ሆነው ለሚያጠናቅቁ የመጽሐፍ ሽልማት እንዲሁም
🏆በአጠቃላይ ውድድሩ ከ1-3 ለሚወጡ ዳጎስ ያለ የገንዘብ ሽልማት ተዘጋጅቷል።

🏵በተጨማሪም ለሁሉም የውድድሩ ተሳታፊዎች የምስክር ወረቀት ይሰጣል!

ውድድሩ ላይ ለመሳተፍ ከታች ባለው ሊንክ ይመዝገቡ
👇👇👇
https://forms.gle/gqVoNDphT3ekdAEk6

NB:
📍ውድድሩ ለሁሉም ሙስሊሞች ክፍት ነው። የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሁሉም ካምፓስ ተማሪ፣ የሌላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ እንዲሁም ከውጭም ተማሪ የሆነም ያልሆነም መሳተፍ ይችላል።
📍ውድድሩ የሚደረገው በኦንላይን በ6 ኪሎ ጀመዓ የቴሌግራም ቻናል ላይ ነው።

©️ 6 Kilo Jemea

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

02 Dec, 03:48


የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የጠቅላላ ጉባዔውን አካሄደ!

•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

ከተመሠረተ 3 አመታትን ያስቆጠረውና በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሙስሊም ተማሪዎችን የጋራ ችግሮች ጀመዓዎችን በህብረት በማቆም እንዲፈቱ እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የዩኒቨርሲቲ ጀመዓ አሚሮች በተሰባሰቡበት ከህዳር 20/2017 ዓ.ል እስከ ህዳር 22/2017 ዓ.ል የጠቅላላ ጉባዔውን በአዲስ አበባ አካሂዷል:: ህብረቱ  ከፌደራል መጅሊስ እውቅና ያገኘ ሲሆን በጉባዔው ባለፉት 3 አመታት የሰራቸውን ስራዎች ገምግሞ የወደፊት አቅጣጫውን አስቀምጧል:: በጠቅላላ ጉባዔው ላይ በተለይም ከመብት ትግል እንቅስቃሴ ጋር የተለያዩ ጥናታዊ ፅሁፎች የቀረቡ ሲሆን የመፍትሔ አቅጣጫም ተቀምጧል::

በመጨረሻም ጉባዔው የተለያዩ አመራሮችን መርጦ ተጠናቋል:: አላህ መልካም ለውጥን ያመጡ ዘንድ እንዲያግዛቸው ዱዓችን ነው!

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!

https://t.me/EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

30 Nov, 07:08


ዛሬ 1⃣1⃣:0⃣0⃣ ሰአት ላይ ይጠናቀቃል


የሲራራ አዋርድ 3 ሚሊዮን ብር አሸናፊ ለመሆን የተወሰኑ ሰአታት ብቻ ይቀራሉ። ስለዚህ እስከ አሁን ላይክ ያላደረጋችሁ ታች ባለው ሊንክ በመግባት ዒልማ ኮሌጅ ሀሳብ ላይ ላይክ በማድረግ ለ ኮሌጁ ምስረታ ደማቅ የሆነ አሻራችሁን እንድታሳርፉ እንጠይቃለን። ይህ የ ዒልማ ኮሌጅ የምስረታ ሀሳብ የቀረበው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የ 6 ኪሎ ጀመአ አሚርና የ4ኛ አመት የፖለቲካል ሳይንስና አለም አቀፍ ግንኙነት ተማሪ በሆነው ኢስማኢል አብዱሮ አማካኝነት ነው።

Sa'aati 1⃣1⃣:0⃣0⃣ irratti goolabama

Dorgommiin Siraaraa Badhaasa qarshii Miiliyoona 3 injifachuuf sa'aatii muraasa qofatu hafa. Kanaafuu namoonni hanga ammaatti like hin godhin like gochuun hundeeffama Koolleejjii ILMAA kana keessatti Ashaaraa keessan akka kaahattan isin gaafanna. Yaanni hundeeffama Koolleejjii ILMAA Amiira Jama'aa barattoota Musliima Yunivarsiitii Finfinnee Campus 6-kilo fi Barataa waggaa 4ffaa Saaynisii Siyaasaa fi Hariiroo Idil-addunyaa Ismaa’il Abdurrootiin kan dhiyaateedha.

like gochuuf/ላይክ👍ለማድረግ👇👇👇

https://web.facebook.com/hijrabanksc/posts/pfbid02kuGG6AcCw53LseXzMnr9MbfA79mZtM2dh857myiBADkobaR44HBQUBdrd52pcRZvl?comment_id=916458207214136

@ismaelabduro

AAU - Muslim Students Union

29 Nov, 12:11


1⃣ ቀን ብቻ ቀረዎው Guyyaa 1⃣ qofatu hafa

የ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት 6 ኪሎ ጀመአ አሚር እና  የ 4ኛ አመት ፖለቲካል ሳይንስ እና አለም አቀፍ ግንኙነት ተማሪ የሆነው ወንድማችን ኢስማኢል አብዱሮ አማካኝነት በ ሂጅራ ባንክ ሲራራ አዋርድ ላይ የቀረበው የ ዒልማ ኮሌጅ ምስረታ የሀሳብ ውድድር ሊጠናቀቅ የ አንድ ቀን እድሜ ብቻ ቀርቶታል። ስለዚህ ሁላችሁም ታች ባለው ሊንክ በ ሂጅራ ባንክ የፌስቡክ ገፅ ላይ በመግባት የ ኢስማኢል አብዱሮን ሀሳብ ላይክ በማድረግ እርሶም ለዚህ እስላምክ ኮሌጅ ምስረታ አሻራቹን እንዲትጥሉ በአክብሮት እንጠይቃችኋለን።

እሱ በሀሳብ እኛ በላይክ እናሸንፋለን

Obboleessi keenya Amiira Yunivarsiitii Finfinnee Campus 6-kilo kan ta'e fi barataa PSIR waggaa 4ffaa kan ta'e Ismaa’il Abdurroo Dorgommii Sirara irratti yaada Hundeeffama Koolleejjii ILMAA dhiyeesse dorgommiin isaa xumuramuuf guyyaa tokkoo qofatu hafa, kanaafuu namoonni hanga ammaatti like hin godhin link armaan gadii kanaan seenuun like akka gootanii hundeeffama koolleejjii Islamaa kanaaf ashaaraa keessan akka kaahatan waamicha isiniif goona.

ላይክ ለማድረግ👇👇👇
https://web.facebook.com/hijrabanksc/posts/pfbid02kuGG6AcCw53LseXzMnr9MbfA79mZtM2dh857myiBADkobaR44HBQUBdrd52pcRZvl?comment_id=916458207214136

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

29 Nov, 01:46


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Nov, 15:29


2⃣ ቀን ብቻ ቀረዎው  Guyyaa 2⃣  qofatu hafa

የ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት 6 ኪሎ ጀመአ አሚር እና  የ 4ኛ አመት ፖለቲካል ሳይንስ እና አለም አቀፍ ግንኙነት ተማሪ የሆነው ወንድማችን ኢስማኢል አብዱሮ አማካኝነት በ ሂጅራ ባንክ ሲራራ አዋርድ ላይ የቀረበው የ ዒልማ ኮሌጅ ምስረታ ሀሳብ ሊጠናቀቅ የ ሁለት ቀን እድሜ ብቻ ቀርቶታል። ስለዚህ ሁላችሁም ታች ባለው ሊንክ በ ሂጅራ ባንክ የፌስቡክ ገፅ ላይ በመግባት የ ኢስማኢል አብዱሮን ሀሳብ ላይክ እንዲሁም ለሌሎች ሼር በማድረግ ሀሳቡን ላይክ እንዲያደርጉለት በማድረግ ይሄን ወንድማችንን እንድትተባበሩት በአክብሮት እንጠይቃችኋለን።

እሱ በሀሳብ እኛ በላይክ እናሸንፋለን

Obboleessi keenya Amiira Yunivarsiitii Finfinnee Campus 6-kilo kan ta'e fi barataa Saaynisii Siyaasaa fi Hariiroo Idil-addunyaa waggaa 4ffaa kan ta'e Ismaa’il Abdurroo Dorgommii Sirara irratti yaada Hundeeffama Koolleejjii ILMAA dhiyeesse dorgommiin isaa xumuramuuf umrii guyyaa lamaa qofatu hafe, kanaafuu namoonni hanga ammaatti like hin godhin link armaan gadii kanaan seenuun like akka gootaniif isin yaadachiisna.

ላይክ ለማድረግ👇👇👇
https://web.facebook.com/hijrabanksc/posts/pfbid02kuGG6AcCw53LseXzMnr9MbfA79mZtM2dh857myiBADkobaR44HBQUBdrd52pcRZvl?comment_id=916458207214136

©ismaelabduro

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Nov, 10:14


በማይመለከትህ ጉዳይ አትግባ!

ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿من حُسنِ إسلامِ المرءِ تركُه ما لا يَعْنيه.﴾

“የአንድ ሰው ከእስልምናው ማማር የማይመለከተውን ነገር መተዉ ነው።”

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

28 Nov, 03:27


﴿يَا أَيُّهَا النَّاسُ قَدْ جَاءَتْكُم مَّوْعِظَةٌ مِّن رَّبِّكُمْ وَشِفَاءٌ لِّمَا فِي الصُّدُورِ وَهُدًى وَرَحْمَةٌ لِّلْمُؤْمِنِينَ﴾

"እናንተ ሰዎች ሆይ! ከጌታችሁ ግሳጼ በደረቶች ውስጥም ላለው (የመጠራጠር በሽታ) መድኃኒት ለምእምናንም ብርሃንና እዝነት በእርግጥ መጣችላችሁ፡፡" (ዩኑስ 57)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

27 Nov, 14:36


ማስታወሻ!

ነገ ሐሙስ ነው። የቻልን እንጹም፤ ያልቻልን መልዕክቱን እናሰራጭ!

عن عائشة رضي الله عنها قالت : كان النبي صلى الله عليه وسلم يتحرَّى صوم الإثنين والخميس
ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዓንሃ) እንዲህ ብላለች፦ "ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) ሰኞና ሐሙስ መጾምን ያዘወትሩ ነበር" (ቲርሚዚ፤ ኢብኑ ማጃህና ነሳኢ ዘግበውታል)

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

27 Nov, 03:34


﴿وَالْبَاقِيَاتُ الصَّالِحَاتُ خَيْرٌ عِندَ رَبِّكَ ثَوَابًا وَخَيْرٌ أَمَلًا﴾.

"መልካሞቹም ቀሪዎች ጌታህ ዘንድ በምንዳ በላጭ ናቸው፡፡ በተስፋም በላጭ ናቸው፡፤" (አል-ከህፍ 46)

ዑስማን ኢብኑ አፋን፡- "መልካሞቹ ቀሪዎች ምንድናቸው?" በማለት ተጠየቁ። እሳቸውም፦ "ከአላህ በቀር ሌላ አምላክ የለም፣ ክብርና ጥራት ለአላህ ይገባው፣ ምስጋና ለአላህ ይገባው፡ አላህ ታላቅ ነው፣ ከአላህም በቀር ምንም ኃይልም ብርታትም የለም። ናቸው" አሉ።

«سُبْحَانَ اللهِ ، وَالحَمْدُ للهِ ، وَلَا إلَهَ إلَّا اللهُ ، وَاللهُ أكْبَرُ ، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إلَّا بِاللهِ»

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

25 Nov, 15:02


ኢልማ ኮሌጅ ልሸልም ነው ብሏል!

  በወንድማችን ኢስማኢል አብዱሮ ሀሳብ አመንጪነት ተወጥኖ በሲራራ አዋርድ የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ የቀረበው የኢልማ ኮሌጅ ፅንሰ- ሀሳብ በሐጅራ ባንክ የሀሳብ መስጫ ሳጥን ላይ ላይክ አድርገው ላይክ ለሚያስደርጉ 20 ሰዎች ልዩ የሆኑ ሽልማቶችን እንካችሁ ብሏል::

ተሸላሚ ለመሆን:-

■ በትንሹ 10 ሰዎች የኢስማኢል አብዱሮን የFacebook ገፅ foollow እንዲያደርጉ: የኢልማ ኮሌጅ ምስረታ ሀሳብን በሒጅራ ባንክ የፌስቡክ ገፅ ላይ በመግባት Like እንዲያደርጉ ማስደረግ

■ ፎሎው እና ላይክ ያስደረጋችሁበትን screenshot ከታች ባሉት አድራሻ መላክ

ሽልማቶች:-

■ ብዙ ሰዎችን Like ያስደረጉ 3 ሰዎች ከ15ሺህ እስከ 5ሺህ የሚዘልቅ ሽልማት እንዲሁም ኮሌጁ ሲቋቋም በስማቸው በፈለጉት ከተማ ቅርንጫፍ መክፈት እንዲሁም ለተቀሩት 17 ሰዎች የተለያዩ ሽልማቶች

ላይክ ያስደረጋቹትን ስክሪንሹት በዚህ ላኩልን
https://forms.gle/azpysEHkVdgs8AiL8

Hijra Bank comment section link
https://www.facebook.com/share/p/Lmcr9tbcyrJpf9g8/

Ismael Abduro's Facebook page
https://www.facebook.com/profile.php?id=61556497600845&mibextid=JRoKGi

ውድድሩ ከህዳር 15 ጀምሮ እስከ ህዳር 21, ከ ቀኑ 11:00 ድረስ የሚዘልቅ ይሆናል:: መልካም እድል!

©ismaelabduro

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

23 Nov, 16:14


🌟ILMA challenge Award💫

🎉🎉🎉እልማ አዋርድ🎉🎉🎉

ላይክ አድርጎ ሰውን ላይክ ማስደረግ ያሸልማል💸💎

⚡️ላይክ በማድረግና በማስደረግ ተሸላሚ ይሁኑ ይለናል እልማ ኮሌጅ💰
ነገ ህዳር 15, ከቀኑ በ11:00 ሙሉ መረጃውን እላይ ባሉ ቻናሎች  የሚናሳውቃችሁ ይሆናል።

እታች ባለው ሊንክ ላይክ በማድረግ ይጠብቁን🕰

Stay Tuned ❗️❗️❗️

🎗Badhaasa ILMAA 🥇

Like gochuu fi like nama goosisuun nama badhaasisa💵


⚡️Namoota like goosisuun badhaafamaa ta'aa nuun jedha kolleejjiin ILMAA💰

⚡️Guyyaa boruu sadaasa 15, sa'aatii 11:00 irratti guutuu isaa karaa toora channelota gubbaa kanaan kan isin beeksisnu ta'a.
Ofirratti nu eegaa!🎗🎗

Yaada koolleejjii ILMA like gochuuf 👇👇
Ismael Abduro facebook link
https://www.facebook.com/profile.php?id=61556497600845&mibextid=JRoKGi

Hijra Bank comment section link
https://www.facebook.com/share/p/Lmcr9tbcyrJpf9g8/
 
(From The ILMA collage committee )

©ismaelabduro

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Nov, 04:10


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

21 Nov, 05:07


ምዝገባው ተጠናቋል። የተመዝገባችሁ ሁሉ ትምህርቱ ኢንሻላህ በቅርቡ የሚጀመር ይሆናል።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Nov, 14:38


በ አዲስ አበባ ዩኒቨረስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የ6ኪሎ ጀመዓ አሚር የሆነው ወንድማችን  ኢስማዒል  አብዱሮ በሲራራ አዋርድ የስራ ፈጠራ ውድድር ላይ ለመወዳደር ሀሳቡን አቅርቧል::

እና ሁላችሁም ከታች ባለው link በመግባት ሀሳቡን አይታችሁ በሒጅራ ባንክ የኮሜንት ሳጥን ላይ ላይክ ታደርጉ እና አስተያየት ትሰጡ ዘንድ ጋበዝኳችሁ!👇

Obboleessi keenya Amiirri Jama'aa Barattoota Musliima Yunivarsiitii Finfinnee Campus 6-kilo baankii hijraa irratti dorgommii business plan dorgomaa jira waan ta’eef fuula Facebook hijra bank link armaan gadii kanaan seenuun comment isaa like akka gootan isin affeera.

👇👇👇👇 like his comment.

https://www.facebook.com/share/p/6DT5WApuMg12fG5K/

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

19 Nov, 14:14


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከነሲሓ አካዳሚ ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የተከታታይ የሸሪዓ ትምህርት ምዝገባ ነገ የሚጠናቀቅ ይሆናል።

ያልተመዘገባችሁ ወንድሞችና እህቶች አሁንም እድሉ ስላለ መመዝገብ ትችላላችሁ!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

19 Nov, 14:12


وَقُلِ ٱعْمَلُوا۟ فَسَيَرَى ٱللَّهُ عَمَلَكُمْ وَرَسُولُهُۥ وَٱلْمُؤْمِنُونَ ۖ وَسَتُرَدُّونَ إِلَىٰ عَـٰلِمِ ٱلْغَيْبِ وَٱلشَّهَـٰدَةِ فَيُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمْ تَعْمَلُونَ

Tell ˹them, O  Prophet˺, “Do as you will. Your deeds will be observed by Allah, His Messenger, and the believers. And you will be returned to the Knower of the seen and unseen, then He will inform you of what you used to do.”

በላቸውም ሥሩ አላህ ሠራችሁን በእርግጥ ያያልና፡፡ መልክተኛውና ምእምናንም (እንደዚሁ ያያሉ)፡፡ ሩቁንና ቅርቡን ሁሉ ዐዋቂ ወደ ኾነውም (አላህ) በእርግጥ ትመለሳላችሁ፡፡ ትሠሩትም የነበራችሁትን ሁሉ ይነግራችኋል፡፡

“Hojjadhaa; Rabbiin, ergamaan Isaatiifi mu’uminoonnis fuula dura dalagaa keessan ni argu. Gara beekaa wantoota hin mul’anneefi wantoota mul’ataniis fuula dura ni deebitu. Waan isin dalagaa turtanis isinitti odeessa” jedhi.

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Nov, 15:27


በአዲሱ የAAU ተማሪዎች ዲሲፕሊን መመሪያ ዙሪያ የህብረቱ እንቅስቃሴ እና የዩኒቨርሲቲው አቋም!

የሙስሊም ተማሪዎችን መብት የሚረግጠው መመሪያ ከወጣ ጊዜ አንስቶ የአዲስ አበባ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከተለያዩ አካላት ጋር በሰላማዊ መንገድ መፍትሔ ለማምጣት ሰፊ እና ጥልቅ ውይይቶችን ሲያደርግ ቆይቷል:: መጀመሪያ ላይ መመሪያው የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ረግጦ ተግባራዊ ሊደረግ በተሞከረበት እለት 6ኪሎ የነበሩ የጀመዓ ተወካዮች ከዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ያደረጉ ሲሆን የዚያኔ አመራሮቹ እንደ ምክንያት የጠቀሱት "ሴኩላሪዝም!" የሚለውን ሰበብ ነበር::

ውይይቱ ያለመስማማት ተቋጭቶ የነበረ ሲሆን በ2ኛው ውይይት ላይ አመራሮቹ ሴኩላሪዝም የሚለውን ምክንያት ሙሉ ለሙሉ "ኒቃብ የደህንነት ስጋት ነው!" ወደሚል ቀየሩ:: ስብሰባው ላይ የነበሩ የህብረቱ ተወካዮች ኒቃብ የደህንነት ስጋት እንደማይሆን በምክንያት እና በማስረጃ ሙግት ሲያቀርቡ እዚያው በዚያው ያንን ምክንያት በመተው "ኒቃብ ክላስ ውስጥ በመምህሩ እና በተማሪዋ መካከል የሚኖረውን መናበብ ያከብደዋል:: ኒቃብ የምትለብስ ተማሪ ሙሉ ለሙሉ መሳተፍ ይከብዳታል::" ወደሚል ቀየሩ:: ለዚህም ውሃ ለማይቋጥር ሰበብ የህብረቱ ተወካዮች አሳማኝ መልስ በማቅረባቸው ውይይቱ ያለስምምነት ተቋጭቶ የመጨረሻ መፍትሔ ለማምጣት ዩኒቨርሲቲውም ሆነ ህብረቱ የመፍትሔ ሀሳብ ይዘው እንዲመጡ ቀጠሮ ተያዘ::

በዚህም ውስጥ ህብረቱ ከአዲስ አበባ መጅሊስ ጋር በመወያየት የደህንነት ስጋት እና የተማሪዎችን ማንነት መለየት አይቻልም ለሚሉት ማሳበቢያዎች መጅሊሱ ሙሉ ወጪውን ሸፍኖ ለዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን በጣት አሻራ የሚለይበትን ቴክኖሎጂ እንደሚያስገባ ዝግጁ መሆኑን ገልፆ ህብረቱ እንደመፍትሔ ሊያቀርብ በተያዘለት ቀጠሮ ዝግጁ ሆኖ ሳለ ዩኒቨርሲቲው የቀጠረውን ቀጠሮ አልወያይም በማለት ሰረዘ:: ከዚያም ቡሃላ ዩኒቨርሲቲው ያወጣውን መመሪያ ሁለት ጊዜ ያሻሻለ ሲሆን ምክንያት ከመቀያየር ውጭ መብታችንን የሚረግጡ ድንጋጌዎችን አላስተካከለም:: ህብረታችንም መፍትሔ ፍለጋ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ከአዲስ አበባ እና ከፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጋር ውይይቶችን አድርጓል:: እንደ መፍትሔም በቅርቡ አጠቃላይ አቅጣጫ የሚያስቀምጥ ይሆናል::

በዚህ ውስጥ እኛ እንደ ሙስሊም ተማሪዎች የሃይማኖታችንን ድንጋጌ ተከትለን እየደረሰብን ያለውን የመብት ጭቆናና ረገጣ በሰላማዊ መንገድ ልንፈታ መጓዛችን ሰላም ወዳድ ከመሆናችን እንጅ ከፍርሃት እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል:: በመብታችን በተለይም እምነት ሃይማኖታችንን አስታኮ በሚመጣ ጭቆና ፈፅሞ አንደራደርም:: ሃይማኖታችን የተፈጠርንበት ብሎም የምንኖርለት እና የምንሞትለት እንቁ የሁለት ሀገር ሀብታችን ነው:: የሚከፈለውን መስዋዕትነት ከፍለን መብታችንን እናስከብራለን:: መብታችንን ሊረግጡ የሚመጡ አካላትንም ተጠያቂ እንዲሆኑ እናደርጋለን::

ነፃነት በነፃ አይገኝም!

ጥያቄ አለን!!
መልስም እንፈልጋለን!!


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!!!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Nov, 03:12


የኢስላም ጥላቻ ወይስ የደህንነት ስጋት?

እነዚህ ከላይ የተያያዙት ሁለት ምስሎች በሁለት ሳምንት ውስጥ ሁለት ጊዜ ከተሻሻለው አዲሱ የተማሪዎች ዲሲፕሊን መመሪያ የተወሰዱ ናቸ።

የመጀመሪያው በጥቅምት 12፣ 2017 ዓ.ል ለዩኒቨርሲቲው ሴኔት እንዲጸድቅ የቀረበው የተማሪዎች ዲስፕሊን መመሪያ ነው። በዚያም ላይ ኒቃብን "ከደህንነት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ማንነትን ለመለየት ሲባልና ከፀጥታ ጋር በተገናኘ ምክንያት" በሚል ከለከለ።

ነገር ግን ጥቅምት 28፣ 2017 ዓ.ል (ከሁለት ሳምንት በኃላ) "ደህንነት" የምትለዋ ሰብብ ጊዜ ያለፈባት መሆኑን ሲረዱ የክልከላውን ምክንያት ወደ "መማር ማስተማርና አገልግሎት ጋር በተያያዘ" ወደሚል ተቀየረ።

ከዚህ በላይ የኢስላም ጥላቻ ምን አለ?!

ዩኒቨርሲቲው አላማውን ግልጽ አድርጓል፤ "ምክንያት ኖረም አልኖረም መብታችሁን እጋፋለሁ" ብሏል።

እኛም እንላለን፡-
#ጥያቄ_አለን #መልስም_እንፈልጋለን!!

መቼም ወደኃላ አንልም፤ መቼም እጅ አንሰጥም!!


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Nov, 03:04


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሁንም በድጋሚ ጥቅምት 28 አዲሱን የተማሪዎች የስነምግባርና የዲሲፕሊን ደንብ ለሁለተኛ ጊዜ እንደገና ያሻሻለ ቢሆንም፤ አሁንም ግን የሙስሊም ተማሪዎችን ቅሬታና ጥያቄ ችላ በማለት የኒቃብና የጀመዓ ሰላትን አሁንም ከለክላለሁ እያለ ነው።

እኛም እንላለን፡-
#ጥያቄ_አለን #መልስም_እንፈልጋለን!!

መቼም ወደኃላ አንልም፤ መቼም እጅ አንሰጥም!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Nov, 03:06


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 18:53


ምስጋና ለአለማቱ ጌታ ይገባውና የዛሬ የGrand Da'wa ፕሮግራም ደስ በሚል ሁኔታ ተካሂዷል። ምንም ቢሆን ከሰው ልጅ ስራ ጉድለት አይጠፋምና በፕሮግራሙ ላይ ያያችኃቸውን ጥሩም ይሁን መጥፎ ጎኖች ለወደፊት የተሻሉ ፕሮግራሞችን ለማዘጋጀት ይጠቅሙናልና 2 ደቂቃ በመውሰድ ከታች ያለውን ፎርም እንድትሞሉ እንጋብዛለን።

link: https://forms.gle/o6Wa6QpMeLZJEtqu9

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 14:45


ታላቅ የምስራች ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በኢብኑ መስዑድ ኢስላሚክ ሴንተር ስር ከሚገኘውና ከዚህ በፊት በሐገራችን የሸሪዓ በተለይም የተውሂድ እውቀትን በማስፋፋት ሰፊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ከነበረው ነሲሃ አካዳሚ ጋር በመተባበር ልዩ የሆነ ተከታታይ የሸሪዓ ትምህርት እንዳዘጋጀ ሲገልፅ ከታላቅ ደስታ ጋር ነው:: አጠቃላይ ትምህርቱ ለሶስት ወራት የሚቆይ ሲሆን የፊቂህ፣ ሀዲስ፣ አቂዳ እና ተጅዊድን የመሳሰሉ ወሳኝ እና ቁልፍ የሆኑ እስላማዊ የትምህርት ዘርፎችን አካቶ ይዟል።

አጠቃላይ ትምህርቱ በበይነ- መረብ (Online) የሚሰጥ ሲሆን ትምህርቱን በተገቢው ሁኔታ ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ከAAU ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት እና ከነሲሃ አካዳሚ የጋራ የምስክር ወረቀት የሚያገኙ ይሆናል።

ለመመዝገብ፡ https://forms.gle/3tfAJdYGjjx7i1p39

ለማንኛውም ጥያቄ እና አስተያየት በ @Aaumuslimstudentsunion1 ያናግሩን።

የዚህ ልዩ የእውቀት ማዕድ ተቋዳሽ በመሆን እወቅትዎን ያሰፉ ዘንድ ጋበዝንዎ። ለሚወዱት ሁሉም በማጋራት ውዴታዎን ይግለፁ።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 11:43


በአአዩ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በተዘጋጀው Grand Da'wa - 1 ላይ የቀረበው ፓምፍሌት አማርኛ እና Afaan Oromoo

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 10:28


ማስታወሻ፡-
📌 ፓምፍሌቱ ላይ የቁርዓንና ሐዲስ ጥቅሶች ስላለው ቆሻሻ ቦታ አይጣልም!!

📌 Paamfileeticha irratti jechi Qur'aanaa fi hadiisaa waan jiruuf eddoo balfaa yookiin Xuraawaattii hin gatamu!!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 09:18


الحمد لله الذي بنعمته تتم الصالحات

ፕሮግራሙ ባማረ ሁኔታ ተጠናቋል። ለፕሮግራሙ ስኬት የተረባረባችሁ ሁሉ የአአዩ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ላቅ ያለ ምስጋናውን ያቀርባል።

ኢንሻላህ በሌሎች ተመሳሳይ ፕሮግራሞች የምንገናኝ ይሆናል።

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 08:49


ኡስታዝ ሙሐመድሐሰን ማሜ እጅግ ጥዑም የሆነ ዳዕዋ አድርገውልናል። አሁን ደግሞ ወንድም ሙስዓብ አጠር ያለ መልዕክት ለማስተላለፍ መድረኩን ይዟል።

https://youtube.com/live/WhJh8cjkRYQ?feature=share

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 07:49


ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ አጭር መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን አሁን ደግሞ ኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ መድረኩን ተረክብዋል።

https://youtube.com/live/WhJh8cjkRYQ?feature=share

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 07:34


https://youtube.com/live/WhJh8cjkRYQ?feature=share

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 07:22


The program has started

https://www.youtube.com/live/xdQGGytx7ZQ?si=BFnbdvL9axrpAxgA

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 04:37


only 1 hour left....

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

10 Nov, 03:28


እግሮች ሁሉ ወደ አል-አቅሷ መስጂድ ያመራሉ

2 ሰዓታት ብቻ ቀሩ!!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

09 Nov, 18:51


Assalaamu alaykum warahmatullaahi wabarakatuh.
Guyyaa Borii sanbata guddaa sa'aa 2:30 irraa kaasee hanga sea,6:00 tti turu saganttaa gorsa guddaa irraa argannu ustaazoota keenya jaalatamoofi kabajamoo ta'aniin qophaa'ee dhufaatii keenya qofa eegaa Jira.
Sagantichiis
1, Sheeka keenya abbaa keenya kanta'an gamttaa barattoota muslimaa university finfinnee wajjin yeroo dheeraa kanturan shee sa'iidiin gorsa abbummaa Kan nuuf dabarsaan yootahu.
Itti aansuun Sheeni keenya Kan gorsi isaanii dhagahamee hinquufamne ustaz Hasan maammeetiin Mataduree taqwallaah jedhu irratti gorsa Kan nuuf kennanu Taha Dhuma irrattis obboleessi keenya musab Ahmad itti aanaa gamttaa barattoota muslimaa university finfinnee kantureefii bara darbe medalia warqiitiin Kan eebbifame iccitii milkaaina Isaa Kan nuuf qoodu Taha.
Kanaaf wol argaa keenya Bor ganama masjiida aqsatti haagodhannu.barattoota Lideta,bishoftu,saferaselam,xuqur anbesaa irraa dhufaniif geejjibni qophaa'ee Jira.
Hafuu mitii barfachuunuu Nama gaabbisiisa.

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

09 Nov, 18:25


A few hours left....

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

09 Nov, 07:54


ቀጠሯችን ነገ እሁድ ከጧቱ 2:30 ነው!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የሚዘጋጀውና ለዚህ አመት የመጀመሪያ የሆነው ታላቁ የዳዕዋ ፕሮግራም ሊዘጋጅ የዛሬን ማለፍ ብቻ እየጠበቀ ነው:: ነገ እሁድ ከጧቱ 2:30 ጀምሮ ከታላላቅ እንግዶች ጋር ልዩ የሆነ ቆይታ አፍንጮ በር በሚገኘው አል- አቅሷ መስጂድ ይኖረናል:: በፕሮግራሙ ላይ ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ የመክፈቻ ምክር ያደርጋሉ:: ኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜ ሰፋ ያለ ሙሐደራ ያቀርባሉ:: ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በወርቅ ሜዳሊያ የተመረቀው ወንድም ሙስዓብ አህመድ የህይዎት ተሞክሮውን ያቀርባል:: ሌሎች አነቃቂና አስተማሪ ፕሮግራሞችም የሚኖሩን ይሆናል::

በሰዓቱ እንገኝ!
ላልሰሙት እናሰማ!!
ለሌችም share እናድርግ!!!


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

08 Nov, 11:52


2 ቀናት ብቻ ቀርተውታል!

በዚህ አመት ለመጀመሪያ ጊዜ የሚሰናዳው Grand Daewa program ሊካሄድ የ2 ቀናት እድሜ ብቻ ቀርቶታል። ፕሮግራሙ ለየት ብሎ የተዘጋጀ ሲሆን የ2017 ዓ.ል አዲስ ገቢ ተማሪዎችን ከሲንየር ወንድም እህቶቻቸው ጋር ያገናኛል። "እንኳን በደህና መጣችሁ! እንኳንም በደህና ቆያችሁን!" በመባባል ውስጥ ከትልልቅ አሊሞችና ቱባ ልምድ ካላቸው ወንድሞች ምክር እውቀት እና ልምድ ይጋራሉ::

በግቢም ሆነ ከግቢ ውጭ ለሚኖረው ህይዎት ትልቅ ስንቅን ይሰጣልና ቀጠሯችንን ቀጠሯችሁ ታደርጉ ዘንድ ጋበዝን:: በመጪው እሁድ ከጧቱ 2:30 በአል- አቅሷ መስጅድ ሰብሰብ ብለን እንድመቅ::

ላልሰሙት እናሰማ!
ለሁሉም ይደርስ ዘንድ ለሁሉም Share እናድርግ!!


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

08 Nov, 06:24


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

07 Nov, 12:15


3 ቀናት ብቻ ቀሩት!

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የሚዘጋጀው ታላቁ የGrand ዳዕዋ ፕሮግራም ከታላላቅ እንግዶቹ ጋር ሊካሄድ 3 ቀናት ብቻ ቀርተውታል!!

ሁላችንም እንገኝ፣ እናሰራጭ

ቀን፡ እሁድ ኅዳር 01፤ 2017 ዓ.ል
ሰዓት፡ ከጠዋቱ 02፡30 - 06፡00
ቦታ፡ ስድስት ኪሎ፣ አል-አቅሷ መስጂድ

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

06 Nov, 06:56


🎉ልዩ የቅዳሜ እና እሁድ የበጋ ስልጠና በኢሙዳት(የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ዳዕዋና ትምህርት ማህበር)🎉


    ኢሙዳት በየአመቱ በክረምት እና በበጋ ወቅት አጠቃላይ የንፅፅር እውቀት ብልፅግና ላይ የሚያተኩሩ ስልጠናዎችን ያለ ምንም ክፍያ በታዋቂ ኡስታዞች እና አሰልጣኞች በመስጠት ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅ ይታወቃል።

በመሆኑም በዘንድሮ የበጋ ልዩ የሆነ ስልጠና በዋነኝነት ከዚህ ቀደም በማንኛውም ሁኔታ የንጽጽር ትምህርት መሰረት ያላቸውን እና በሃይማኖት ንጽጽር  ዘርፍ ለኢስላም መስራት የሚፈልጉ 2ኛ ደረጃ ት/ት ተማሪዎች፣ ለዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ  በተጨማሪም በማንኛውም ዘርፍ ላይ ያሉ ወጣቶችን ለይቶ ስልጠናዎችን ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል። 

    ስልጠናው የሚያጠነጥነው የንፅፅር እውቀት፣ ኢማንን ማጎልበት፣ የሊደርሽፕ ፣ አርት እና ኢስላማዊ ስልጣኔ፣ የማህበረሰባዊ አይዲዮሎጂዎች እና መሰል የወጣቶችን ንቃተ ሕሊናን የሚያጎለብቱ ጉዳዮች ላይ ሲሆን ስልጠናውም ቅዳሜ እና እሁድ ለግማሽ ቀን ከህዳር እስከ ሰኔ መጨረሻ ድረስ የሚቆይ ይሆናል።

    በመሆኑም ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉ ትምህርቱን በቋሚነት መከታተል የምትችሉ ወጣቶች (ወንድ እና ሴት) ይህንን ቅፅ በመሙላት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

🏢ኢሙዳት(የኢትዮጵያ ሙስሊም ዳእዋና ትምህርት ማህበር)

🕹ፒያሳ

02:30-06:00LT

ለበለጠ መረጃ ☎️
0944078334
0945728270
                              ይደውሉ።

ማጋራት አይርሱ

🛑ያለን ቦታ ውስን ነው።

🎉የመመዝገቢያ Link👇

https://forms.gle/xuGxGbhnmtPzWdyd8

AAU - Muslim Students Union

05 Nov, 08:05


ታላቁ የዳዕዋ ፕሮግራም 5 ቀናቶች ብቻ ቀርተውታል!

ሁላችንንም ከየካምፓሱ አሰባስቦ የወንድም እህትማማችነት ፍቅርን የሚያላብሰው Grand Daewa ፕሮግራም ደርሷል:: መለያችን የሆነው Grand ዳዕዋ ፕሮግራም ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርተውታል:: እንዋደድ እንቀራረብ እንማር እንማማር ዘንድ ከ5 ቀናት ቡሃላ በሚመጣውና በሚያሰባስበን ታላቅ የዳዕዋ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ እናቅድ::

በፕሮግራሙ አባታችንና መካሪያችን ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ እንደሚገኙ እሙን ነው:: ኡስታዝ ሙሐመድ ሐሰን ማሜም በጥዑም ዳዕዋቸው የፕሮግራማችን ድምቀት ይሆናሉ:: በወርቅ ሜዳሊያ አጊጦ የተመረቀው የቀድሞው የህብረታችን ም/አሚርም ስለ ስኬት ጉዞው የሚያስቃኘን ይሆናል:: ፈገግታን በመጫር እያስተማሩ ፍቅርን የሚዘሩ አነቃቂ ፕሮግራሞችም ተሰናድተዋል::

ስለሆነም በመጪው እሁድ እንገናኝ!
ቀጠሯችንን በአል-አቅሷ መስጂድ እናድርግ!
ከጧቱ 2:30 ስብስብ ብለን እምር ይበልብን!

ከሰፈረ-ሰላም: ልደታ: ጥቁር አንበሳ እና ቢሾፍቱ ለምትመጡ ወንድም እህቶች ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

03 Nov, 03:37


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በድጋሚ ለሙስሊሙ ያለውን ንቀት አሳይቷል!!

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ አዲሱን የተማሪዎች የስነምግባርና የዲሲፕሊን ደንብ እንደገና ያሻሻለ ቢሆንም፤ አሁንም ግን የሙስሊም ተማሪዎችን ቅሬታና ጥያቄ ችላ በማለት የኒቃብና የጀመዓ ሰላትን አሁንም ከለክላለሁ እያለ ነው።

እኛም እንላለን፡-
#ጥያቄ_አለን #መልስም_እንፈልጋለን!!

መቼም ወደኃላ አንልም፤ መቼም እጅ አንሰጥም!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

02 Nov, 14:29


ታላቅ የዳዕዋና ሙሐደራ ፕሮግራም!

እነሆ ቀን ቀናትን ተክቶ የዚህ አመት የመጀመሪያው ታላቅ የዳዕዋ እና የአዲስ ገቢ ተማሪዎች አቀባበል ፕሮግራም (AAUMSU GRAND DA'WA - 1) ከተለያዩ ጣፋጭና ልዩ ትዝታን አሳርፈው ከሚያልፉ ፕሮግራሞችጋ ሊከናዎን ቀናት ብቻ ቀርተውታል:: በፕሮግራሙ

📌 አባታችን እና መካሪያችን የሆኑት ሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ የእንኳን መጣችሁ መልዕክት ያስተላልፉልናል፤

📌 በጣፋጭ ዳዕዋቸውና ምክራቸው የምናውቃቸው ሸይኽ ሙሐመድሐሰን ማሜ "አሏህ መፍራት" በሚል ርዕስ ዳዕዋ ያደርጉልናል።

📌 የጀመዓችን ምክትል አሚርና በ2016 ዓ.ል የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ የነበረው ወንድማችን ሙስዓብ አህመድ "በአካዳሚና ዲን እንዴት መላቅ እንችላለን?" በሚል ርዕስ ልምዱን ያካፍለናል።

ከፕሮግራም መቅረት አይደለም፤ ማርፈድ ያስቆጫል!!

ፕሮግራሙ:-
🗓 እሁድ ኅዳር 01/2017 ዓ.ል
🕌 6ኪሎ አፍንጮበር በሚገኘው ታላቁ አቅሷ መስጂድ ይካሄዳል::
2:30 ጀምሮ 6:00 ይጠናቀቃል::

🔺 ከሰፈረ-ሰላም፣ ቢሾፍቱ፣ ጥቁር አንበሳና ልደታ ለሚመጡ ተማሪዎች ትራንስፖርት ተዘጋጅቷል::

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

01 Nov, 03:04


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

26 Oct, 11:18


⭐️⭐️ AAUMSU GRAND DA'WA & WELCOME PROGRAM ⭐️⭐️

COMING SOON...


💫 With big guests
💫 With big topics
💫 With big ideas


🚀 Stay tuned❗️❗️

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

26 Oct, 05:49


ዋ ኢስላማ!!!

የኛ ነገር ይገርማል! ያሳዝናልም!! ያስለቅሳልም!!!


ሁልጊዜም አጀንዳዎቻችን ለአንድ ሳምንት ብቻ ይቆያሉ፤ ከዚያም ይረሳሉ። የሙስሊሞች መብት ተገፈፈ ሲባል ለአንድ ሳምንት እንጮሃለን፤ ከዚያስ? የግል ጉዳይ እንድጂ የዲን ጉዳይ እስካይመስል ድረስ ይረሳል!! ይተዋል!! መብታቸው የተገፈፈው ወንድም እና እህቶችም ልባቸው ተሰብሮ ይቀራል። አዲስ አጀንዳ ሲመጣ ያም እንደዚሁ ይሆናል!!!!

ይህ አመት ከገባ ባለፉት ሁለት ወራት ብቻ ምን እንደተፈጠረ እንመልከት፦

📌 ሸይኻ ፋጢማ የአይነ ስውራን አዳሪ ትምህርት ቤት በሙስሊሞች ተሰርቶ ሳለ ግቢ ውስጥ አትሰግዱም፤ ሂጃብ ለብሳችሁ አትንቀሳቀሱም በማለት ተማሪዎቹን አባረረ፤ ሚዲያውም ለአንድ ሳምንት ጮኸ። ከዚያስ? ተረሳ፤ እህት እና ወንድሞቻችን ተባረው ቀሩ!!

📌 ይህንኑ ድክመታችንን የተገነዘበ የሚመስለው የትምህርት ቤቱ አመራር ምንም ሳያፍር የትምህርት ቤቱን ስም ቀየረ፤ እኛም ለአንድ ሰሞን ጮኸን ዝም አልን። እነሱም ቀጠሉና በሐገሪቱ ሐብት በሚተዳደር ቴለቭዥን ላይ በይፋ መለወጣቸውን አሳዩ፤ እኛም ዝም አልን!!!!

📌 ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ከዚህ በፊት ሲጠቀሙበት የነበረውን የካፌ በር በመዝጋትና ከሃይማኖታቸው የአመጋገብ ስርዓት ውጪ ሴቶች ከወንዶች ጋር ተቀላቅለው እንዲመገቡ አደረገ፤ የግቢውን በር መክፈቻና በዝጊያ ጧት 12:00 እና ከማታም 12:00 በማድረግ ተማሪዎች የሱብሂ: መግሪብ እና ኢሻዕ ሶላትን ከመስጂድ እንዳይሰግዱ ከለከለ፤ ከዚያም አልፎ ዶርም የሚሰግዱ ተማሪዎችን ማሳደድ ጀመረ፤ ይባስ ብሎም ተማሪዎች ችግራቸው እንዲፈታ በሰላማዊ መንገድ ሙከራ በሚያደርጉ ጊዜ በግቢው የሚገኙ የፀጥታ አካላት የተለያዩ ማስፈራሪያዎችንና ዛቻዎችን ማድረስ ጀመሩ። ይህ ሁሉ ሲሆን አንድም የሙስሊሙ ጉዳይ ይመለከተኛል ብሎ የተንቀሳቀሰ አካል የለም!!! ሁላችንም ጸጥ ረጭ!!!

📌 ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የኢሻዕ ሰላት ሰግደው ሊገቡ ሲሉ "ኒቃብ፣ ጀለብያ እና አማኢማ ለደህንነት ስጋት ናቸው" በማለት ኒቃብና ጀለብያ ለብሳችሁ አትገቡም አሉ፤ ተማሪዎችን በዱላ ለማስፈራራትና ለመበተን ሞከሩ። ይህ ሲሆን ግን አንድም ለተማሪዎች መብት ሊቆም የተነሳ አካል የለም!!!

📌 የኛው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ "የደህንነት ስጋት" በማለት ኒቃብን ሊከለክል ሞክረ፤ ኒቃብ ለባሽ እህቶችን ለማዋከብ ሞክረ፤ ሁላችንም ለአንድ ሰሞን ጨኸን፤ ለጊዜው ጉዳዩ ረገበ፤ ከዚያም ሁላችንም ረሳነው፤ የኛን መተኛት አሰፍስፎ የሚጠብቅ አካል እንዳለ ዘነጋን!!!

📌 አሁን ደግሞ አዲስ ከተማ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላለፉት ሶስት አመታት ኒቃብ ለብሰው ሲማሩ የነበሩ ተማሪዎችን ወይ አውልቁ ወይ ትምህርት ቤት አትምጡ አለ፤ 11 የሚሆኑ እህቶችንም አባረረ፤ ነገር ግን ይህ ሁሉ ሆኖ ተማሪዎቹን ሊያግዝ ፈቃደኛ የሆነ ማንም አካል የለም፤ ሁሉም ወደኃላ መሸሽን መረጠ!!

እኒህ እንግዲህ ባለፉት ሁለት ወራት ከተከሰቱት የምናውቃቸው ብቻ ናቸው፤ የማያውቀውን ብንጨምር...

እስከመቼ ነው አጀንዳ ተቀባይ ሆነን የምንቀጥለው? እስከመች ነው የሙስሊሙን መብት እንዲያከብሩ የተቀመጡ አካላት በዝምታቸው የሚቀጥሉት?

አሁንማ የለመድንው ይመስላል!!! የመብታችንን መገፈፍ የተቀብልነው ይመስላል!!

ንቁ ያ ኡመተ ሙሐመድ!!!!


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

26 Oct, 03:16


Last Chance To APPLY!!!

ለስድስት ወራት የሚቆየው የዳሩል አርቀም የአመራርነት ስልጠና ፕሮጀክት ምዝገባ ሊጠናቀቅ አንድ ቀን ብቻ ይቀረዋል።

🔻ለመመዝገብ ፡ ይህን ይጫኑ!

ዳሩል አርቀም የአመራርነት ፕሮጀክት

©6 Kilo Jemea

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

25 Oct, 03:01


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Oct, 07:55


🎉ልዩ የቅድመ ትዳር ስልጠና በ 6 ኪሎ ጀመዓ!!!🎉🎉

አሰላሙዓለይኩም ወራሕመቱላሂ ወበረካቱህ።

የ 6 ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአይነቱ ልዩ የሆነ የቅድመ ትዳር ስልጠና በ ኦንላይን ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቅቆ ምዝገባ መጀመሩን ሲገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።

ትዳር የአላህ (ሱ.ወ) ስጦታ ነው። የፍጥረተ ዓለሙ አሰራርም ጭምር ነው። የብቁ ማሕበረሰብ ግንባታ ከስኬታማ ቤተሰብ ይጀምራልና ረጅሙን የህይወት ጉዟችንን ለማስዋብ ወጣቱ መሰል ስልጠናዎችን መውሰዱ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል። በመሆኑም፦

📌 ትዳር ምንድን ነው?
📌 የጋብቻ ጥቅም ምን ይመስላል?
📌 ከትዳር በፊት ምን ዓይነት ዝግጅት ያስፈልጋል?
📌 በትዳር ውስጥ ሊገጥሙን የሚችሉ መሰናክሎች ምን ምን ናቸው? እንዴትስ እንወጣቸዋለን? ••• በሚሉትና በሌሎችም ንዑስ ርዕሶች ዙሪያ በዘርፉ የካበተ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች ባላችሁበት ሆናችሁ በኦንላይን ትሰለጥኑ ዘንድ ግብዣችንን እንካችሁ እንላለን። ይህንን ወሳኝ ስልጠና በመካፈል መጭው ህይወታችሁን ከአላህ ጋር ብሩህ ለማድረግ ተከታዩን የቦት ሊንክ በመጠቀም ተመዝገቡ። የስልጠናውን ሰዓት እና ሊንክ እንዲሁም ሌሎች ዝርዝር መረጃዎችን ከምዝገባ በኋላ በውስጥ የምናሳውቃችሁ ይሆናል።

ከባባድ ውሳኔዎች ከእውቀት በኋላ መወሰናቸው ትርጉሙ ጥልቅ ነው!

ቅድመ ስልጠና የዳሰሳ ጥናት ቦት
።write your name and your Telegram username 👇👇👇
@skmsj_fb_bot

©️ 6 kilo Jeme'ah

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

22 Oct, 03:16


🗣🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ👋👋

ወድ የ4ኪሎ ግቢ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ እኚህ ከላይ የተዘረዘሩ መፅሀፍት በጀመዓችን የሚገኙ መፅሀፍት ናቸው። መፅሀፍትን የማንበብ ልምድ የአስተሳሰባችንን አድማስ ለማስፋት ከሚያገለግሉ ትልልቅ መሳሪያዎች ውስጥ አንዱ ነው። እኚህን መፅሀፍት ለማንበብ የምትፈልጉ ተማሪዎች በ +251992546811 ወይም @AbuUsamaZeya1 ላይ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን
ለወንዶች በሰላት ጊዜያት እንዲሁም ለእህቶች ከመግሪብ እስከ ኢሻ ባለው ጊዜ ወይም በሴቶች ተወካዮች በኩል የሚደርሳቹ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን።

© 4 kilo Jeme'ah

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

21 Oct, 10:59


🗣Good News

📎The tejrid kitab will start today after magrib In shaa Allah

📎Those registered through the form will get their books then

👉Share it to your friends

© 5 kilo Jeme'ah

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Oct, 17:50


🎉🎉 ታላቅ የምስራች ለ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች 🎉🎉

በ 6 ኪሎ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ አነሳሽነት የሚካሄደው "የዳሩል-አርቀም የአመራርነት ስልጠና" ፕሮጀክት ለሁለተኛ ዙር የተማሪዎች ምዝገባ መጀመሩን ሲገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።

ፕሮጀክቱ በመጀመሪያው ዙር ከተለያዩ ካምፓሶች የተውጣጡ 40 ገደማ ተማሪዎችን  ተቀብሎ ለስድስት ወራት ካሰለጠናቸው በኃላ በደማቁ ማስመረቁ ይታወሳል።

ይህ ሙስሊም ተማሪዎችን በያሉበት ዘርፍ መሪ እና ተጽእኖ ፈጣሪ እንዲሆኑ ማስቻልን አላማው አድርጎ የተነሳው ፕሮጀክት ባለፈው ዙር የተመዘገቡ ስኬቶችን እና ለውጦችን በማየት ራሳቸውን ለመሪነት ብቁ ማድረግ ለሚፈልጉ ጥቂት ተማሪዎች በሮቹን በመክፈት አርሂቡ ይላችሗል።

ፕሮጀክቱ ዘርፈ ብዙ ስልጠናዎችን፣ ሙሃደራዎችን፣ የንፅፅር ትምህርቶችን፣የልምድ ልውውጥ መድረኮችን፣ የመጽሃፍ ዳሰሳዎችን እና የጉብኝት ፕሮግራሞችን የያዘ ሲሆን ሙስሊም ተማሪዎች ያላቸውን የመምራት አቅም እንዲያውቁና እንዲጠቀሙ ለማድረግ የታሰበ ነው።

በመሆኑም የዚህ ፕሮግራም አካል መሆን  የሚፈልግ ተማሪ የሚከተለውን ፎርም በጥንቃቄ በመሙላት ለሰልጣኝነት እንዲታጭ በአክብሮት እንጋብዛለን።

ለመመዝገብ click me

መልካም እድል!
ዳሩል አርቀም የአመራርነት ፕሮጀክት

© 6Kilo Jeme'ah


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Oct, 05:43


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጀመረው ሙስሊም ተማሪዎችን ከሃይማኖታዊ እሴታቸው የማራቅ እና ሃይማኖታዊ መብታቸውንና ነፃነታቸውን የመንጠቅ እንቅስቃሴ መልኩንና ይዘቱን በመቀየር ሰሌላ ዩኒቨርሲቲ እና ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲም ደርሷል:: ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ የግቢው በር 12:00 የሚዘጋ በመሆኑ ከግቢ ወጥተው ሶላት መስገድ የማይችሉ ተማሪዎች ከግቢ ውስጥም ሆነው እንዳይሰግድ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው ነው:: ካፌም ላይ ከዚህ በፊት ከነበረው ሁኔታ በተቃራኒ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሃይማኖታቸው ከሚያዛቸው የአመጋገብ ስነ-ስርዓት ውጭ ተቀላቅለው እንዲመገቡ በመደረግ ላይ ነው::

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ደግሞ ኒቃብ: ጀለብያ: አማኢማ እና መሠል በእስልምና የሚታዘዙ አለባበሶችን "ለደህንነት ስጋት ስለሆነ መልበስ አትችሉም!" በማለት ተደጋጋሚ የሆነ ወከባ በማድረስ ላይ ይገኛሉ:: ተማሪዎችም "ከዚህ በፊት ስንለብስ የደህንነት ስጋት ሳንሆን ቀርቶ አሁን ምን ተገኝቶ ነው? ይህ ሃይማኖታዊ ግዴታችንና የዜግነት መብታችን ነው::" በማለት ስለ እስልምናቸውና የነፃነት መብታቸው ጥያቄያቸውን ለዩኒቨርሲቲው አቅርበዋል::

በአላህ ፈቃድ የሚያስፈልገው መስዋዕትነት ሁሉ ተከፍሎ በሁሉም ቦታ በየትኛውም ጊዜ መብታችን እንዲከበር ልንተጋ ግድ ይለናል:: ዛሬ እኛ እያለፍንበት ያለውን ሁኔታ ልጆቻችን እንዲኖሩት መፍቀድ የለብንም::

©️EHEMSU

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

20 Oct, 03:39


"አላህ በሕዝቦች ዘንድ ያለውን ጸጋ በነፍሶቻቸው ያለውን (ኹኔታ) እስከሚለውጡ ድረስ አይለውጥም፡፡ " (አር-ረዕድ 11)

ኢብን ጀሪር አጥ-ጠበሪ ስለዚህች አንቀጽ ሲያብራሩ እንዲህ ይላሉ፦
"ሰዎች እርስ በእርሳቸው በመበዳደልና አንዱ በአንዱ ላይ ድንበርን በማለፍ በነፍሶቻቸው ያለውን ኹኔታ እስከሚለውጡ ድረስ አላህ በነርሱ ዘንድ ያለውን በረከት እና ደህንነት በማንሳት አይለውጥም"

የአት-ተፍሲር አል-ወሲጥ ጸሐፊም እንዲህ ይላሉ፦
"ከዚያም አላህ -ጥራት ይገባውና - ከማይለወጡ ሱናዎቹ አንዱን ሲጠቅስ እንዲህ አለ፡- (በእርግጥ አላህ የሰዎችን ሁኔታ በነፍሶቻቸው ውስጥ ያለውን ነገር እስኪለውጡ ድረስ አይለውጥም) ማለትም ስዎች ራሳቸውን (ስራቸውን፤ ባህሪያቸውን ወዘተ...) ከታዛዥነት ወደ ወንጀል፤ ከቆንጆ ወደ አስቀያሚ፣ ከማስተካከል ወደ ማብላሸት እንስካልቀየሩ ድረስ አላህ - ክብር ለርሱ ይገባው - የሰዎችን ፀጋ፣ ድህንነት እና መልካም ሁኔታ ወደ ተፃራሪው አይለውጥም"

በእርግጥም ጌታችን እውነትን ተናግሯል፤ በሐገራችንም ሆነ በዓለም ላይ ሙስሊሙ ላይ ለሚደርሰው ግፍ የመጀመሪያው መንስዔዎች እኛው ራሳችን ነን!

ከአላህ ዲን ስንርቅ፤ ኃሳብችን ሁሉ ዱንያ ሲሆን፤ አላህ የዚህ ዑማ መገለጫ ያደረገውን በጥሩ ማዘዝን እና ከመጥፎ መከልከልን ስንተው አላህ ውርደትን አከናነበን!

አሁንም መፍትሄው አንድ እና አንድ ብቻ ነው፤ ወደ አላህ በንጹህ ተውባ መመለስ፤ በዲናችን ጉዳይ ላይ የአቅማችንን ያክል መሳተፍ፤ የእውቀት ሓለቃዎችን ማብዛት፤ በአላህ ዲን ጉዳይ እስከመጨረሻው መታገል ብቻ!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

19 Oct, 05:59


የ4ኪሎ ካምፓስ የ2017 ዓ.ል የመጀመሪያ ሴሚስተር ደርስ ፕርግራም

ሁሉም ደርሶች የሚሰጡት ኢኽላስ ህንጻ ምድር ቤት በሚገኘው የ4ኪሎ ተማሪዎች መስጂድ ነው። 4ኪሎ እና አካባቢው ያላችሁ ልጆች ይህ እድል እንዳያመልጣችሁ ተጠቀሙበት

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

18 Oct, 12:27


ወሳኝ መልዕክት ከዛሬው የጁምዓ ኹጥባ

በሸይኽ ሰዒድ አህመድ ሙስጠፋ


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

18 Oct, 03:17


﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)

"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)

اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

17 Oct, 14:54


"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ድምጾቻችሁን ከነቢዩ ድምጽ በላይ ከፍ አታድርጉ፡፡ ከፊላችሁም ለከፊሉ እንደሚጮህ በንግግር ለርሱ አትጩሁ፡፡ እናንተ የማታውቁ ስትኾኑ ሥራዎቻችሁ እንዳይበላሹ (ተከልከሉ)፡፡" (አል-ሑጁራት 2)

ይህች አንቀጽ በወረደች ጊዜ ሳቢት ኢብን ቀይስ የሚባል ሰሃባ ጠንካራ ድምጽ ያለው በመሆኑ ይህች አንቀጽ በእርሱ ላይ የወረደች መሰለው፤ ሁለተኛም ድምጹ ከእርሳቸው ድምጽ ከፍ እንዳይል በመፍራት ነብዩን ላለማግኘት በቤቱ ውስጥ ራሱ ላይ ቀለፈ። የአሏህ መልዕክተኛም ከሰሃቦቻቸው መካከል ሲያጡት "ሳቢት የት ነው?" ብለው ጠየቁ። ሰሃቦችም የሆነውን ነገሯቸው፤ ነብዩም እንዲጠራ በማድረግ "ምስጉን ህይወትን በመኖር፤ ሸሂድ ሆኖ በመሞት ጀነት መግባት አያስደስትህምን?" አሉት። እርሱም "በአሏህ እና መልዕክተኛው ብስራት ተደስቻለሁ" አላቸው።

ሰሃቦች እንደዚህ ነበሩ፤ እነዚያ ብርቅ ትውልዶች አኽላቃቸው እንደዚህ ነበር። ከአሏህ ወቀሳ ሲመጣ ወደሌሎች ሳይሆን ወደራሳቸው ነበር የሚመለከቱት፤ ራሳቸውን ነበር የሚፈትሹት።

የኛስ ትውልድ? አሏህ ከጠበቀው በስተቀር አብዛኞቻችን ጀነት እንደምንገባ ከአሏህ መተማመኛ የተሰጠን እስኪመስል ድረስ የራሳችንን ዓይብ ትተን የሌሎችን ዓይብ በመከታተል ላይ ተጠምደናል፤ ራሳችንን ረስተን የሰዎችን ስራ መዛኝ ሆነናል!!!

عجبت لمن يبكى على موت غيره
دموعا ولا يبكى على موت قلبه دما
وأعجب من ذا أن يرى عيب غيره
عظيما وفى عينيه عن عيبه عمى

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

17 Oct, 03:16


"በእርሱ ውስጥ ያስታወሰ ሰው የሚገሰፅበትን እድሜ አላቆየናችሁምን? አስጠንቃቂውም መጥቶላችኋል።" (ፋጢር 37)

አስጠንቃቂው በሚል በዚህ አንቀጽ የተጠቀሰው የዘምዶች ሞት መሆኑን ከፊል ሙፈሲሮች አብራርተዋል።

መች ይሁን የምንገሰጸው፤ መች ይሁን ወደአላህ ዲን የምንመለሰው፤ መች ይሁን ወደመስጂድ መሄድን የምናዝወትረው፤ መች ይሁን ዲናችንን በአግባቡ መማር የምንጀምረው?

ባለፈው አመት ብቻ ከዚሁ ከግቢያችን ተማሪዎች 6 ያህሉ ተራቸው ደርሶ ወደማይቀረው ቀጠሮ ሄደዋል፤ ያውም የተወሰኑት ያለምንም በሽታ ባላሰቡበትና ባልገመቱት አጋጣሚዎች።

ቀጣይ እኛ እንደማንሆን ምን ማረጋገጫ አለን? ወድ አላህ የምንመለስበት ጊዜ አልደረሰምን? አላህ ፊት ቆመን ዲኑን ለመርዳት ምን አደረክ ስንባል ምን ብለን ልንመልስ ነው?

"ከመካሪም ሞት ይበቃል!"

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Oct, 13:34


አዲሱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጨቋኝ መመሪያ ከየት እስከ የት?

በነሐሴ 2016 ዓ.ል የወጣውና የሙስሊም ተማሪዎችን መሠረታዊ የአለባበስ ብሎም የአምልኮ ተግባራት ከሚከለክለው መመሪያ ጋር ተያይዞ ጀመዓችን የአአዩ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን አድርጓል:: መመሪያው የሴት ልጆችን ኒቃብ እንዲሁም የጀመዓ ሶላትንና የሶላት መስገጂያ ቦታ መጠየቅን በግልፅ የሚከለክል በመሆኑ የዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች እንደማይቀበሉት በተደጋጋሚ ገልፀዋል::

ይህንንም ተከትሎ እስካሁን ባለው ሂደት ህብረታችን የሙስሊም ተማሪዎችን ጥያቄ ከበታች አመራሮች እስከ ዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት አድርሷል:: ከፕሬዚዳንት ፅ/ቤት አመራሮች ጋር በተደረገ ውይይትም ዘላቂ መፍትሔ እስኪደረግ ድረስ ከለከልን ያሉትን ከለከልን ከማለታቸው በፊት ባለው ሁኔታ እንዲቀጥል ስምምነት ላይ የተደረሰ ቢሆንም ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ተይዞ የነበረውን ቀጠሮ ዩኒቨርሲቲው ባቀረባቸው ተቀባይነት በሌላቸው ምክንያቶች ሳቢያ ተሰርዞ መፍትሔ ሳይደረግለት ቀርቷል::

ሆኖም አሁንም ቢሆን ሙስሊሙ ተማሪ እንዲያውቅ የምንፈልገው ነገር ቢኖር በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ኒቃብም ሆነ ሌሎች መሠረታዊ ሀይማኖታዊ መብቶችን በነፃነት መተግበር እንደምንችል ነው:: እነርሱ ከዚህ በፊት መመሪያ አውጥተው ሊከለክሉን ሲሞክሩ አልተቀበልናቸውም:: ዛሬም ቢሆን ከትላንት የተለየ ቀንም ሆነ ሁኔታ የለም:: ዛሬም ቢሆን ስለነፃነታችን የምንደራደርበት ምንም ምክንያት የለም:: ዛሬም ቢሆን መብታችንን ለእነርሱ ፍላጎት አሳልፈን አንሰጥም::

በእነርሱ በኩል የተለያዩ ምክንያቶችን ከመደርደር ባሻገር ነገሩ ተድበስብሶ እንዲቀር የተለያዩ መንገዶችን እየቀየሱ ነው:: ይህ የተለመደው አካሄዳቸው ሆኖ ሳለ ከእኛ በኩል መብታችንን የሚደፈጥጡ ድንጋጌዎች ከመመሪያው ተሰርዘው እስኪወጡ ድረስ መታገል ግድ ይለናል:: በዚህ ረገድ ህብረታችን መፍትሔ ለማምጣት ሲል ከተለያዩ አካላት ጋር በመነጋገር ላይ ነው:: ከዚህ ጋር በተያያዘ ተማሪያችን ጉዳዩን ጉዳዬ ብሎ ሌት ተቀን ከማስታወስና ዱዓ ከማድረግ ባሻገር እህቶቹን በማበርታትና እርስ በዕርስ በመጠነካከር ይበረታ ዘንድ አደራ እንላለን::

ይህ የአላህ መንገድ ነው:: መንገዱም የፍትሕ የነፃነት እና የድል መንገድ ነው::

አአዩ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት !

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

16 Oct, 11:04


"(እናንተ በአላህ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ!) በእውነቱ የእነዚያ ከበፊታችሁ ያለፉት ምዕመናንን ያጋጠመ መከራ የመሰለ ሳይመጣባችሁ ገነትን ልትገቡ ታስባላችሁን? መልዕክተኛውና እነዚያ ከእርሱ ጋር ያመኑት 'የአላህ እርዳታ መቼ ነው?' እስከሚሉ ድረስ መከራና ጉዳት ደረሰባቸው። ተርበደበዱም። አስተውሉ የአላህ እርዳታ በእርግጥ ቅርብ ነው ተባሉም።" (አል-በቀራህ 214)

ስኬትና ድል በቀላሉ ያለ ትግል አይገኙም፤ ጀነት በቀላሉ አትገኘም፤ መታገልና መታገስን ትጠይቃለች። አሏህን ምዕመና 'የአላህ እርዳታ መቼ ነው?' እስከሚሉ ድረስ ይፈትናቸዋል።

መብታችን ለማስከበር በምናደርገው ትግል ላይ ስኬት እንቀዳጅ ዘንድ ልክ ከኛ በፊት የነበሩት ምዕመናን እንዳደረጉት ሁሉ ወደአሏህ ልንመለስ ይገባል!

ስለእህትህ የኒቃብ መብት እየታገልክ ከአጅነብይ ጋር የምትጃጃል ከሆነ ነስር እንዴት ይመጣል?
ስለእህትህ የኒቃብ መብት እየታገልክ አሏህ ያዘዘክን የጀመዓ ሰላት የማትሰግድ ከሆነ ነስር ከየት ይመጣል?
ስለእህትህ የኒቃብ መብት እየታገልክ ስለዲንህ ምንም የማታውቅ ከሆንክ ነስር ከዬት ይመጣል?

ስለእህትሽ የኒቃብ መብት እየታገልሽ ከአጅነብይ ወንድ ጋር የምትጃጃይ ከሆነ ነስር እንዴት ይመጣል?
ስለእህትሽ የኒቃብ መብት እየታገልሽ እስልምና ለሴት ልጅ ያዘዘውን የአለባብሰ ስርዓት የማትከተይ ከሆነ ነስር እንዴት ይመጣል?
ስለእህትሽ የኒቃብ መብት እየታገልሽ የዲን እውቀት ለመማር ተነሳሽነት ከሌለሽ ነስር ከየት ይመጣል?


አሏህ የመጨረሻውን አሸናፊነት ለሙዕሚን ባሮቹ እንደሚያደርግ ቃል ገብቷል። ጥያቄው እኛ ከነዚያ ውስጥ ነን ወይ ነው!!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Oct, 14:28


የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ዙሪያ ባወጣው ጨቋኝ መመሪያ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል::

ጥያቄ አለን!!
መልስም እንፈልጋለን!!


@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Oct, 13:48


የደርስ ማስታወቂያ!

የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ኪታብ እነሆ ከቀጣይ ሰኞ ጀምሮ በሸይኻችን ሸይኽ አብዱረሂም ሙሳ ለተማሪዎች በልዩ ሁኔታ የሚጀመር ስለሆነ ሁላችንም የዚህ እድል ተጠቃሚ እንሁን!!!

ደርሱ የሚሰጥበት ቀን፡ ሰኞ፣ ማክሰኞ እና እሮብ
ሰዓት፡ ከመግሪብ እስከ ዒሻዕ
ቦታ፡ አል-አቅሷ መስጂድ

የምዝገባ ሊንክ፡ link

©️5Kilo Jama'ah

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Oct, 11:33


Afaan Oromoo

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Oct, 11:31


For fresh students, check out this info to know about the activities of our Jama'ah

©️6Kilo Jama'ah

Share it with others too

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Oct, 07:11


«ሕዝቦቼም ሆይ! ጌታችሁን ምሕረትን ለምኑት፡፡ ከዚያም ወደርሱ ተጸጸቱ፡፡ ዝናብን በእናንተ ላይ ተከታታይ አድርጎ ይልክላችኋልና፡፡ ወደ ኃይላችሁም ኃይልን ይጨምርላችኋል፡፡ አመጸኞችም ሆናችሁ አትሽሹ፡፡» (ሑድ 52)

ጌታችን እውነትን ተናገረ!! በጠላቶቻችን ላይ ጉልበት ባጠረን ጊዜ፤ ምድርም ከስፋቷ ጋር በጠበበችን ጊዜ፤ የኢስላም ጠላቶች በኛ ላይ በተረባረቡ ጊዜ ወደ አሏህ ከመመለስ ውጪ ምንስ አማራጭ አለን?

ጌታችንም የምትለምኑኝና ወደእኔ የምትመለሱ ከሆነ "ወደ ኃይላችሁም ኃይልን ይጨምርላችኋል" በማለት ቃል ገባ፤ "በንግግርም ከአላህ ይበልጥ እውነተኛ ማን ነው?"

በበትግላችን ስኬት እንቀዳጅ ዘንድ ወደአሏህ በፀፀት እንመለስ፤ ምህረትን እና ድልን እንለምነው!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

15 Oct, 05:28


ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ገቢ ሙስሊም እህት ወንድሞቻችን:-

በመጀመሪያ የአላህ ሰላም እዝነት እና ረድዔት በእናንተ ላይ ይሁን :: ምስጋና ሁሉ ሁሉንም ችግር አልፋችሁ በውጤት ለእዚህ ስኬት እንድትበቁ ላስቻለው ጌታችን አላህ የተገባ ይሁን :: እንደ አንድ ሰውነት ሆነን እንድንደጋገፍ እና እንድንረዳዳ ባስተማሩን አዛኙ ነብይ ላይም የአላህ ውዳሴ እና ሰላም ይስፈን ::

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ሙስሊም እህት ወንድሞቹን በኢስላማዊ ፍቅር እና እንክብካቤ አቅፎ ለመቀበል ዝግጅቱን አጠናቋል :: ስለሆነም እናንተ እህት ወንድሞቻችን ከምንም በላይ ከደም በላይ የሚያጋምደንን የኢስላም እህት ወንድማማችነት በማሰብ ማንኛውም የምትፈልጉትን መረጃ እና እገዛ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች በኩል ትጠይቁ ዘንድ እንጠይቃለን ::
    
📌 AAU MUSLIM STUDENTS UNION - 0909524252

Main and FBE Campus
📌 ኢስማዒል አብዱሮ - Main campus - 0936906322
📌 አብዱረሂም አሚን  - FBE Campus - 0995477358

AAiT (5 Kilo) Campus
📌 ማህፉዝ ነጋሽ - AAIT - 0996220264

4 Kilo Campus
📌 ዘይድ ሳዲቅ - 4kilo - +251992546811
📌 መስዑድ ውበቱ - 4kilo - +251905877461

Sefere Selam Campus
📌 ሙሐመድአሚን - s.selam campus - 0917046439
📌 ኑር አወል - s.selam campus - ++251951044287

Ldeta Campus
📌ያህያ አባ ረሻድ - Ldeta Campus - 0965435476 or 0777435476
📌 አብዱልዓዚዝ ሙሄ - Ldeta Campus - 0909534342 or 0777534342

https://t.me/aaumsu

AAU - Muslim Students Union

14 Oct, 14:51


የጥንቃቄ መልዕክት!

"የአላህን ብርሃን በአፎቻቸው ሊያጠፉ ይሻሉ፡፡ አላህም ከሓዲዎቹ ቢጠሉም እንኳ ብርሃኑን ገላጭ ነው፡፡" (አስ-ሰፍ 8)

ነገ እና ከነገ ወዲያ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ወደ ግቢ ይገባሉ። በዚህም መሐል የግቢ ጥበቃዎች ልክ ከዚህ ቀደም ሲያደርጉ እንደነበረው ሙስሊም ተማሪዎችን በተለይም ኒቃብ ለባሽ እህቶችን አዲስ በመሆናቸው ለማዋከብ ይሞክራሉ።

ሁላችንም ይህ እንዳይሆን መከላከል አለብን፤ በየግቢያችን መግቢያ በሮች ላይም ይሁን ግቢ እህቶቻችን ላይ የሚደርስ ማንኛውንም በደል ህገ-ወጥ ነውና ልናስቆም ይገባል፤ መረጃ ልንይዝ ይገባል

ከዚህ በኋላ ነገሮችን በትዕግስት የምናልፍበት ምንም ምክንያት የለም፤ ማንም ይሁን ማን ተጠያቂ ይሆናል። በተለይ ተማሪዎችን የምትቀበሉ ወንድሞች እና እህቶች ነገሮችን በትኩረት መከታተል ላይ አደራ!!

@aaumsu

AAU - Muslim Students Union

14 Oct, 12:32


Niqab Update!!

ስለአዲሱ መመሪያ ዩኒቨርሲቲው ከህብረታችን ጋር ለዛሬ ይዞት የነበረውን ቀጠሮ አላከበረም:: ለቀጠሮው አለመከበርም የተለያዩ ተቀባይነት የሌላቸውን ምክንያቶች አስቀምጠዋል:: አሁንም ቢሆን በመብታችን እንደማንደራደር እየገለፅን አሁን ስላለው ነበራዊ ሁኔታና ስለቀጣዩ አቅጣጫችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን:: ሁላችሁም መረጃዎችን በንቃት ጠብቁ:: ዱዓም አድርጉ!

@aaumsu