የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች @ne_siha_eslamik Channel on Telegram

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

@ne_siha_eslamik


بسم الله الرحمن الرحيم


📮እንኳን ወደዚህ ቻናል ተቀላቀሉ‼️


በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም ከአረብገንዳ መስጊድ በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው።

ሃሳብ አስተያዬት ካለ በዚህ ያድርሱን ⤵️
@ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች (Amharic)

ሰላም፣ እንኳን እናስመምጥዎት የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች በዚህ ቻናል። ይህ በዚህ ቻናል ቂርአቶችን፣ ሙሐድራዎችን፣ ዳዐዋዎችን እና ሌሎችንም በአሚሩ አማካኝነት በቀጥታ የምታገኙበት ቻናል ነው። ከዚህ የሚመጣው አገልግሎት ከአረብ ገንዳ መስጂድ መረጃዎችን ያቀናል። እርዳታዎችን እና የዚህ ቻናልን ለበለጠ ማሰራጨት ይጠይቃል። ለበለጠ የተዘጋጀውን እርዳታዎችን ለማስጠንክ ወደ @ye_Arebgenda_mesgid_wetatoch_bot ይተላለዋል።

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

16 Jan, 20:24


ሶሀቦች በጁሙዓ ቀን ሰለዋትን ማብዛት ይወዱ ነበር። ሰዎችንም እንዲያበዙ ያበረታቱ ነበር።እንዳውም
አብዱላህ ኢብን መስዑዱ (ረ.ዐ) እንደሚለውም :-
"አንተ ዘይድ ኢብን ወህብ ሆይ! የጁሙዓ ቀን ላይ አንድ ሺ ሶላት አለነቢ ማለትን አትዘንጋ!" ብሎ ጓደኛውን ያበረታታ ነበር።

✍️ ኢብነል ቀይም ረሂመሁላህ.
📕 ጀላኡል አፍሃም

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

16 Jan, 18:33


https://youtu.be/xGuVt0YlLWI

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

14 Jan, 19:39


https://youtu.be/HKlyxPpgjtA

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

13 Jan, 23:05


አላህን ሳንጠይቀው ብዙ ነገር ሰጥቶናል። እንዲሁም በህይወት ስንኖር ጥቂት ነገሮችን እንድንፈፅም ግዴታ አድርጎብናል። ግዴታዎቻችንን በአላህ ፍቃድ ከተወጣናቸው ቀን በቀን እናመስግን። አሁን ካለንበት ደረጃ በላይ እንዲሰጠን ከፈለግን, ግዴታ ካደረገብን ነገሮች በተጨማሪ ወደን እና ፈቅደን ኢባዳ እናድርግ። ..ነገር ግን ግዴታ ያደረገብንን አላህ በፈለገው መልኩ ሳንወጣ ትርፍ የምንጠይቅው ከሆነ ከውስጣችን ጋር ተጋጭተናል እና ራሳችንን እንመልከት፤ ግዴታ ያደረገብንን ሳንወጣ ተጨማሪ አልያም ትርፍ የሆነን ነገር አላህ እየሰጠን ከሆነ ትልቅ የሆነ ፈተና ውስጥ ሰለሆን ሳናባክን ለሚገባው የሚገባውን ነገር ብቻ እናድርግ። ወደ አላህም እንቃረብ🙏

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

12 Jan, 16:26


አላህ በቀጥተኛው መንገድ ላይ ሊያረጋጋህ ሲፈልግ በዱንያ ላይ ችግሮችን በችግር ላይ ደራርቦ ይሰጥህና ምን እንደምታደርግ ይመለከተሃል። ያኔ አስተንታኝ ከሆንክ በትግዕስት ወደሱ መሸሽን ትመርጣለህ!..የዚህም ምሳሌው ወርቅ ወርቅነቱ ጥርት እንዲል ዘንድ በእሳት እንደሚቀልጠው እና ለብቻው ዋጋ እንዳለው እንደሚለየው ማለት ነው!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

09 Jan, 00:36


ልባችን ከመድረቁ የተነሳ አላህ ምንም የማያደርግ ይመስለናል። ጨካኞች ሁሌም በድሎት ላይ እንደበደሉ አይኖሩም። ተበዳዮችም ሁሌ እንደተበደሉ አይቀጥሉም። ምክንያቱም በዚች አለም ሆነ በቀጣይቱ አለም በፍርድ የማያዳላው አላህ(ሱ.ወ) ስላለ!
#join #like #shrae

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

08 Jan, 15:17


https://youtu.be/u9yYj-FkqAs

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

06 Jan, 20:37


አሁን አሁን ላይ ሲታሰብ ምክንያታችን አፈንግጦ የወጣ ይመስላል። ወረርሽኝ ሲነሳ በዚህ ምክንያት ነው ብለን ትንታኔ ለመስጠት እንጂ ወደ አላህ ለመመለስ ስንጣደፍ አንታይም። ጦርነት መጣ ሲባል እንደለመደብን ለትንታኔ እንሯሯጣለን። የጎርፍ አደጋ ተነሳ ሲባል እንደለመደብን የለመደብንን እንጂ አላህ እያስጠነቀቀን እንደሆነ አናስተነትንም። ከዚህም ባስ ብሎ የእሳተ ጎመራ እና የመሬት መንቀጥቀጥን አብሮ አምጥቶብናል። እንደለመዱት ምክንያት ከሚተነትኑ ሳይሆኑ ካሉበት የወንጀል ጫካ ለመውጣት ለተውበት ከሚሯሯጡ ያድርገን🤲

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

05 Jan, 18:33


اَلسَّلَامُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللّٰـهِ وَبَرَكاتُهُ‎🤝

✔️ይሄ ቻናል የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች መረጃ የሚለዋወጡበት መስመር ነው ስለሆነም ይሄንን ቻናል Subscribe በማስደረግ በተቻለ ፍትነት ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ያሰራቹጩ

ለምታደርጉልን ትብብር በአሏህ ስም እናመሰግናለን🙏🙏🙏
    📌 የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች                                                               

🔰ЅнαƦ€ Αи∂ ʝσιи🔰
💢።።።።።።ᴛᴇʟᴇɢƦᴀᴍ።።።።።።።💢
   ⭕️ @arebgendamesjid ⭕️
💢።።።።።።ᴛᴇʟᴇɢƦᴀᴍ።።።።።።💢

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

05 Jan, 11:22


https://youtu.be/am6gVhWuGq4?si=ShrJkDnjNhNQTYy4

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

05 Jan, 09:38


እሁድ ከቀኑ 8:30 በዩትዩብ ቻናላችን ይጠብቁን።
#subscribe #share #like

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

04 Jan, 22:41


እጅህን አንስተህ የምትፈልገውን ጠይቀህ ምላሽ ካልሰጠህ፤ አልሰጠኝም ብለህ ከመበሳጨት ይልቅ, አላህ ሊሰጥህ የፈለገውን ለመቀበል መዘጋጀት ጀምር። ምክንያቱም አንተ ፈልገህ የጠየከውን ካልሰጠህ እሱ የፈለገው ይበልጣልና ..!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

03 Jan, 07:19


https://youtu.be/TQrhGoW6_N8

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

02 Jan, 16:08


ገባ ገባ እያላቹ ያ ጀምዐ

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

02 Jan, 15:48


https://t.me/arebgendamesjid?livestream=97abf30c9f6060adaf

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

02 Jan, 10:53


ሐሙስ ከቁኑ 8:30 በዩትዩብ ቻናላችን ፕሮግራሙ እንዳያመልጦዎ!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

31 Dec, 19:46


እጅህን አንስተህ አላህን ከልብህ ስትጠይቀው ምላሽ ሰጥቶኻል። ነገር ግን ምላሹ አንተ እንደፈለከው ሳይሆን አላህ ላንተ በዱንያም በአኺራም እንዲጠቅምህ ዘንድ በፈለገው መልኩ ነው የሚመልስልህ!..ይህንን ሁሌ እጅህን ስታነሳ አስታውስ!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

31 Dec, 10:35


አላህ ለባሮቹ ምን ያህል እንደሚያዝን በተጨባጭ ብናውቅ ኖሮ የኛን አጉል ምኞት ትተን የሱን ዉሳኔ ብቻ እንቀበል ነበር!😔

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

29 Dec, 15:14


ችግሮችን አላህ ካደራረበብህ ትልቅ ለሆነ ጥሩ ነገር እያዘጋጀህ ነውና ታግሰህ የአላህን ስራ ግዜ ሰጥተህ ተመልከት...የሚገርምን ጥበብ ታገኝበታለህ!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

26 Dec, 12:36


ምላስህ ዚክር ካበዛች አላህ ለጥሩ ነገር እያዘጋጀህ ነው። በተቃራኒው ምላስህ ዚክር ማድረግ ከከበዳት አደጋ ውስጥ መሆን አመላካች ነውና ዚክር ለማለት ታገል። አላህም እንዲያቀልልህ ዱዓ አድርግ!🤲

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

21 Dec, 10:39


አሳቢ እና አስተንታኝ ሰው አላህ ያሰዘዘውን ነገር አሳምሮ ሰርቶ "አላህ ስራዬን ተቀብሎ ይምረኝ ይሆን!" ብሎ ይጨነቃል ፤ ማሰብ እና ማስተንተን ተቅቶት የሚኖር ሰው አላህ የከለከለውን ነገር ያለ ጭንቅ በግዴለሽ እየተገበረ " ችግር የለውም አላህ ይምረኛል! " ብሎ በአጉል ተስፋ የሚኖር ነው!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

20 Dec, 10:51


የጁሙዓ ቀንን በጤና በኢማን ካደረሰን በርግጥም አላህን እንድንጠይቀው ትልቅ እድል እየሰጠን ነው። በጁሙዓ ቀን ጥቂት ሰዓት አለች የምንፈልገውን ብንጠይቀው የሚመልስበት ... ልባቸው ዝንጉ ከሆኑት አንሁን ! ዱዓ እናድርግ በተለይም ከአሱር እስከ መግሪብ ባሉት ሰዓታቶች🤲

...የISLAMINDSET ቤተሰቦችንም አትርሱ!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

19 Dec, 17:03


ሐሙስ ከምሽቱ 3:15 በISILAMNDSET እንገናኝ..ለ1:30 ያህል በቲክቶክ ቆይታ እናደርጋለን ኢንሻአላህ!
ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

16 Dec, 21:06


ወደዚች ህይወት ስንቀላቀል ምንም ሳንይዝ መጣን፤ በዚች ህይወት ላይ ስንኖር ሁሉም ነገር የኛ እንዲሆን ከታች ላይ ኳተን፤ ከዚች ህይወት ስንወጣ ግን የሰበሰብነው ሁሉ ጥለን እንሄዳለን።

ሁላችንም በዚህ ዑደት እናልፋለን!.. ነገር ግን ብልህ ማለት በዚች ህይወት ሲኖር በብልጠት የማይታለፍበትን ግዜ ቀድሞ ያስታውሳል።ከዚያም ባለው ነገር ሁሉ በህይወት ሲኖር ሙሉ ለሙሉ አራግፎ ሞት ሳይለያየው ቀድሞ ካለው ነገር ጋር ይለያያል። ... ያኔ ዳግም እንዳዲስ ሰዎች ሲባነኑ ከእንቅልፋቸው ይህ ሰውዬ ከተለያየው ንብረቱ ጋር በመገናኘት ነፃ ሊወጣ ዘንድ ሰበብ ይሆንለታል።

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

13 Dec, 07:49


የጧት እና የማታ ዚክሮችን ማለት ይለማመዱ። እነዚህ ከላይ የምትመለከቷቸው ዚክሮች ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) በህይወት ዘመናቸው ሲሏቸው የነበሩ ሲሆኑ ጧት ከሱብሂ በኋላ እና ማታ ከአሱር ሶላት በኋላ ማለትን ይልመዱ!

አላሁመ ሶሊ አላ ሙሐመድ ወአላ አሊ ሙሐመድ
__ መልካም ጁሙዓ __
ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

30 Nov, 17:18


መፈፀም ያለበት ነገር አላህ በሚፈልገው ሰዓት እና ቦታ በውስጥ ፍላጎት ካልፈፀምን, መፈፀም ለሌለበት ነገር ነፍሳችን ተስባለች ማለት ነው! ራሳችንን እንመልከት። ራሳችንን ለመመልከት ደግሞ ያሳለፍነውን ህይወታችንን ማስታወስ በቂ ነው።
ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

29 Nov, 12:38


አላህ በተለያዩ ግዜ እና ሰዓታቶች ባሮቹ የሚጠይቁትን የትኛውም ነገር ከትሩፋቱ ይቸራል።በየትኛውም የህይወት ደረጃ ላይ እንሁን የአላህ እዝነቱ በኛ ላይ አይቋረጥም።ነገር ግን ሰዎች ነን እና በዱንያ ስንኖር በኛ አስተሳሰብ ጎደለን ብለን የምናስባቸው ነገሮች አይጠፉም።ለዚህም በተለያዩ ሀዲስ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት በጁሙዓ ቀን ጥቂት ሰዓታቶች አሉ አላህ ባሮቹ የትኛውንም የሚያስፈልጋቸውን ነገር ቢጠይቁት የሚሰጥበት, ይህም ከአሱር ሶላት በኋላ እስከ መግሪብ ሶላት ሰዓት ድረስ እንደሆነ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) አመላክተዋል። ጉዳይ ካላችሁ አላህን ጠይቁ...ኢንሻአላህ ይሰጣችኋል! በዱዓችሁም ወንድማችሁንም አትርሱት!🤲

[ አላሁመ ሶሊ አላ ሙሐመድ ወአላ አሊ ሙሐመድ..!]

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

26 Nov, 09:42


" እኔ በዱንያ ላይ ልክ እንደ አንድ መንገደኛ ዛፍ ስር እንደተጠለለ እንጂ ሌላ አይደለሁም!"

ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ)
➙ እኛ ግን እንደ ረሱል(ሰ.ዐ.ወ) የሆን አይመስለኝም። ስራችን ሁሉ መንገደኛ ሳንሆን ኗሪ የሆን ነው የሚመስለው!..አላህ ይዘንልን🙏

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

18 Nov, 19:25


መሽቶ ሲነጋ እንዲሁም ነግቶ ሲመሽ አላህ ወደ ጀነት እንድንገባ ዘንድ ተጨማሪ አድል እየሰጠን እንደሆነ ስንቶቻችን እናስተውል ይሆን?! ..አሁን አሁንማ እያስፈራኝ መጥቷል, ለምን? ብትሉ አላህ ያዘነለት ሰው ካልሆነ በቀር መሽቶ ሲነጋ በውስጣችን " ጤነኛ ስለሆኩ ጥሩ እንቅልፍ ተኝቼ ተነሳሁ" ብለን የአላህን ሀይል እና ሁሉን ቻይነት የምንረሳ እየመሰለኝ ነው።በተቃራኒው ነግቶ ሲመሽ ደግሞ ምናልባችም ያሳካነው ነገር ካለ በአላህ ፍላጎት ተሳካልኝ ሳይሆን ልክ እንደ ቃሩን "እኔ ኮ እንደዚህ ነኝ በዕውቀቴ አሳካሁ!" የምንል እየመሰለኝ ነው! ...አላህ ይጠብቀንና!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

11 Nov, 11:45


የሆነ ቀን ነበር እኛ የማናውቀው ግን ወደዚህ አለም የመጣንበት፤የሆነ ቀን ነበር የፈተናን ምሬት የቀመስንበት፤የሆነ ቀን ነበር የደስታን ጥግ ያጣጣምንበት። የነበረን ቀን ማስታወስ ግማሽ ሰውነትን የሚጠይቅ ሲሆን ነገር ግን የሆነ ቀን እና ግዜ እንደሚመጣ ተገንዝቦ መዘጋጀት ሙሉ ሰውነትን ይጠይቃል። ይህም የሆነ ቀን አለ ሳናውቀው እንደተወለድነው ድንገት ሳናውቀው የምንሞትበት፤ የሆነ ግዜ አለ አላህ ያለ አስተርጓሚ ስራችንን እያወቀ የሚጠይቅበት...!
...ለሆነ ቀን እና ግዜ ዛሬውኑ ዝግጅት እናድርግ! አይቀርምና ጉዞው.

                   @besira

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

10 Nov, 17:56


https://vm.tiktok.com/ZMhb3jGpG/

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

03 Nov, 21:34


https://youtu.be/gEIXtQyVt6U

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

31 Oct, 02:34


የኢልም አሻራ በጋራ!    #بصمة_العلم

በሸይኽ ሀሰን ሓሚዲን የሚመራው ወሎ መናገሻ ደሴ ከተማ የሚገኘው ሸይኽ አደም ሙሳ ኢስላማዊ ኮሌጅ ላለፉት 4 አመታት ያስተማራቸውን ኡስታዞች እና ዱዓት እሁድ ጥቅምት 24/2017 ዓ.ል ከጧቱ 02:30 ጀምሮ በደሴ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ ያስመርቃል።

በዕለቱ የኮሌጁ መስራች እና የበላይ ጠባቂ የሆኑት ሸይኽ ሀሰን ሓሚዲንን ጨምሮ በርካታ የሀገራችን ኡለማዕ እና ዱዓቶች በክብር እንግድነት የሚገኙ ሲሆን እርስዎም በዚህ ታላቅ እና ታሪካዊ ፕሮግራም ላይ ይታደሙ ዘንድ በአክብሮት ተጋብዘዋል።

ለበለጠ መረጃ
0913366673
0921042700
0910139340

በእነዚህ የማህበራዊ ድህረገጾች ያገኙናል

YouTube
http://surl.li/yrofrq
Facebook
http://surl.li/nvxfhm
Tiktok
http://surl.li/evhnxq
Telegram channel
https://t.me/sheikhademmusacollege
Sheikh hassen hamiddin "fb"
http://surl.li/mpavlb

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

30 Oct, 20:20


አጫጭር እና ጠቃሚ ቪዲዮዎችን ወደናንተ ስንለቅ እንዲደርሶዎ የቲክቶክ ፔጃችንን ፎሎው ያድርጉ!
የቲክቶክ username ➙ islamindset
ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ከላይ የለቀቅነውን የዩትዩብ ማስፈንጠሪያ ሊንክ ይጫኑ....ጀዛኩሙላህኸይረን.
ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

29 Oct, 17:33


https://youtu.be/DYK1VjWU0VE

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

26 Oct, 20:34


የሸይኽ ሙሐመድ አል-አንሲ ፕሮግራም ነገ ማለትም እሁድ ከሰዓት በ11:30 በISLAMINDSET ዩትዩብ ቻናላችን ይለቀቃል..ኢንሻአላህ!

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

26 Oct, 11:16


የሆነ ቀን ነበር እኛ የማናውቀው ግን ወደዚህ አለም የመጣንበት፤የሆነ ቀን ነበር የፈተናን ምሬት የቀመስንበት፤የሆነ ቀን ነበር የደስታን ጥግ ያጣጣምንበት። የነበረን ቀን ማስታወስ ግማሽ ሰውነትን የሚጠይቅ ሲሆን ነገር ግን የሆነ ቀን እና ግዜ እንደሚመጣ ተገንዝቦ መዘጋጀት ሙሉ ሰውነትን ይጠይቃል። ይህም የሆነ ቀን አለ ሳናውቀው እንደተወለድነው ድንገት ሳናውቀው የምንሞትበት፤ የሆነ ግዜ አለ አላህ ያለ አስተርጓሚ ስራችንን እያወቀ የሚጠይቅበት...!
...ለሆነ ቀን እና ግዜ ዛሬውኑ ዝግጅት እናድርግ! አይቀርምና ጉዞው.

ISLAMINDSET.

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

22 Oct, 15:39


https://youtu.be/rbfrcGWTPxU

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

20 Oct, 21:32


https://youtu.be/U7yutUH8o9M

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

19 Oct, 20:19


አንዳከም፣አንሳነፍ...አላህ ቃል የገባልን እሱን ብቻ ካመለክን የዘላለም የስኬት ህይወት ነው። ለምንስ ተስፋ እንቅርጣለን...ሽይጧን የዘላለም ቅጣት ቃል ተገብቶለት ዱንያ ላይ እስካለ ድረስ ተስፋ አይቆርጥም፤ እኛ የአላህ ባርያ ሆነን ያውም የነብዩ(ሰ.ዐ.ወ)ህዝቦች ሆነን ጀነት ቃል ተገብቶልን ለምንስ ተስፋ እንቆርጣለን!!!?...በኢባዳ በርቱ.
ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

18 Oct, 08:36


"ሰውነታችንን አንርሳ፤ ሰው ሆነን ስለተፈጠርን!"
ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

16 Oct, 18:27


https://youtu.be/CpQErkHeC1g
ሙሉ ፕሮግራሙ ተለቀቀ!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

14 Oct, 10:54


ልዩ ድምፅ በሚል አዲስ ፕሮግራም ዘወትር ሰኞ ከቀኑ 8:00 ላይ በISLAMINDSET ይጀምራል። ጥሩ እና ለህይወታችን ገንቢ ፕሮግራም እንደሚሆን ለቤተሰቦቻችን በአላህ ላይ ተስፋ አለን።ከታች ባለው በዩትዩብ ቻናላችን ብትከታተሉት ተጠቃሚ ይሆናሉ!

https://youtube.com/@islamethiopia?feature=shared

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

13 Oct, 06:01


‏قال الإمام الماوردي رحمه اللّٰه :

قال بعض البلغاء :

إنّ الدنيا لا تصفو لشارب ، ولا تفي لصاحب ، ولا تخلو من فتنة ، ولا تُخلي من محنة ، فأعرض عنها قبل أن تعرض عنك ،  واستبدل بها قبل أن تستبدل بك ، فإنّ نعيمها يتنقّل، وأحوالها تتبدّل، ولذاتها تفنى ، وتبعاتِها تبقى.

أدب الدين والدنيا ص (١٧٨)📚

ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

10 Oct, 21:15


እንደዛሬው ባለ ቀን... ለይሉ ጁምዓ ሲሆንና የኸሚስ ጀንበር ወደ ማደሪያዋ ስትሸኝ፤ የመልከ ብዙ ትሩፋት ከንዝ የሆነው የሶለዋት ሞገድ አየሩ ላይ ይናኛል። አላህ ያገራለት አማኝ ደግሞ እንዲህ ባለ ቀን ከእንቅልፍ ተኳርፎ፤ የከውኑን ሞገስ፣ የዓለሙን ዓይነታ የሚያወድሱ ዓይነተ ብዙ ሶለዋቶችን ያለመታከት እየተቀኘ ሌቱን ሕያው አድርጎ ያነጋል።

አዎ! እንደዛሬው ባለ ምሽት ከነፋሱ ጋር የሚነፍሰው ሶለዋት ዳር እስከ ዳር በቅብብሎሽ ሲከረር፤ የዩኒቨርሱ ብሔራዊ መዝሙር የሆነ ያህል ልብ ያሞቃል።
اللَهُمَّ صلِّ وسَلِم وبَارِك على سيدنا محمد (ﷺ)
youtube// @arebgenda_mesjid ​
t.me// @arebgendamesjid
Instagram // arebgenda_mesjid
tik tok //arebgenda_mesjid
Facebook //mesjid5043

በመጎብኘት የማህበረሰብ ሚዲያዎቻችንን በሚለቀቁ ትምህርቶች እና ጠቃሚ ምክሮች ይከታተሉ።
የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች የሚዲያ ማዕከል

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

10 Oct, 10:46


" ኢስላም በህይወታችን እየጠቀመን ነውን!"
ISLAMINDSET ሜንቶር
Episode ➙ 08

እርግጠኛ ነኝ ርዕሱን ስታነቡት አብዘሃኞቻችን ብዙ ነገር እንደጠቀማችሁ ትመሰክሩ ይሆናል። ነገር ግን "የጠቀማችሁን ዘርዝሩት!" ብትባሉ አትዘረዝሩትም። ለምን ቢባል አላህ ያዘነለት ሰው ካልሆነ በስተቀር የአብዘሀኛው ሰው ህይወቱ በአሁን ሰዓት ላይ የተጠቀመውን ከማስተንተን ይልቅ ወደፊት ይጠቅመኛል ብሎ በሚያስበው ነገር ላይ የተገነባ ነው። ለዛ ነው ኢስላም እንደሚጠቅመን ብናምንም አሁናችንን እና ወደፊቲችንን እዚህ ግባ በማይባሉ ነገሮች ምኞታችን ስለተሞላን ኢስላምን ቦታ የማንሰጠው! ...ብንሰጠውም በተግባራችን እንደሚያመላክተን እንደተጨማሪ ነገር የምናስበው!....


የቪዲዮ ዝግጅቱን በቅርብ ቀን ይጠብቁን!
ISLAMINDSET.
#join #like #shrae

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

17 Sep, 18:46


https://youtu.be/en_gxqRbdYI
ማክሰኞ ➙ ከምሽቱ 11:30 ይለቀቃል!

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

26 Aug, 22:31


ማክሰኞ ከቀኑ 11:30
በዩትዩብ ቻናላችን ይጠብቁን!
ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

14 Aug, 18:28


https://youtu.be/JYP1lLmmJQ0?si=2t9_sHS0LN74uNwn

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

08 Aug, 20:53


በጁመዓ ቀናችሁ እጃችሁን አንስታችሁ በዚህ ዱዓ አላህን ለምኑት...ኢንሻአላህ ሩህሩህ የሆነው አላህ(ሱ.ወ) ያስደስተናል።ከዱዓ አንዘናጋ ..ቀኑ ጁሙዓ ነውና! ብዙዎች ያላገኙት አሉ።
ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

05 Aug, 17:52


ሁሉም ነገር ያልፋል።ሲያልፍ ግን ግዜ በክንውን ነው...እንጂ ክንውን በግዜ አይደለም። ሁሉም ነገር ሲፈፀም ግዜን ተከትሎ ነው የሚፈፀመው! አላህ ፈፅሙ ያለንን ስንፈፅም አፈፃፀማችን ግዜ አለው። ለዚያ ነው ግዴታ፣ሱና፣ዋጂብ እንዲሁም ፈረድ የሚባሉት በግዜ ላይ ጥገኛ የሆኑት።ከተገበርናቸው በግዜ ተጠቀምን ይባላል። በተቃራኒው አራም፣ ሙነከር፣ ቢድዓ እንዲሁም ኩፍር የሚባሉት ሰዎች ሲተገብሯቸው ባላቸው ግዜ ላይ ነው። ከተተገበሩ ግዜ ባከተነ ይባላል። አንድ ሰው ግዜውን ከሚያባክኑ ሰዎች ውስጥ ነው, አልያም ግዜያቸውን ከሚጠቀሙ ሰዎች ውስጥ ነው።ልብ በሉ መሀል ሰፋሪ የሚባል ነገር በዚች አለም ላይ እንደሌለ! ለዚያም ነው አላህ ስለሰራነው ስራ የቂያማ ቀን ሲጠይቀን ሁሉም ጥያቄዎቹ ከግዜ ጋር የተያያዙ ናቸው።ለዚህም ረቂቅ ምክንያቱ ግዜ ማለት ህይወት ስለነበረ ነው!
ትክክለኛ ሙስሊም ሁሌም ግዜውን ይጠቀምበታል..ምክንያቱም ለዚያ የአላህ ጥያቄዎች ምላሽ እንዲሆኑት ዘንድ ማለት ነው።

------------------- መልካም ግዜ ------------------
ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

04 Aug, 11:34


https://youtu.be/xUZlyOXX5_8

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

02 Aug, 14:29


https://youtu.be/xUZlyOXX5_8

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

02 Aug, 14:08


ጁሙዓ ከምሽቱ 12:30 በዩትዩብ ቻናላችን ይጠብቁን!
youtube.com/@islamethiopia

ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

01 Aug, 17:55


በየ አመቱ...በየ ወሩ...በየ ሳምንቱ...በየቀኑ...በየሰዓቱ..በየደቂቃው እንዲሁም በየሴኮንዶች አላህ በኛ ላይ እዝነቱን ፀጋው ምህረቱን ይውልልናል። ልባችን ከድንጋይ በላይ ስትደርቅ ከሰጠን ይልቅ በአብዘሀኛው ያልሰጠን ነገር እንዳለ እያስመሰልን አላህን"አልሀምዱሊላህ!!!" ከማለት እንኮራለን።ነገር ግን ልባችን የመርጠቧ ምልክት የትኛውንም የዱንያ ህመም ላይ እንሁን አላህ በሰጠን ፀጋ ስለምንሽር "አልሀምዱሊላህ!!" ከማለት አናርፍም። ምክንያቱም ፀጋውን በውስጡ ላመነ ሰው "አልሀምዱሊላህ!" እንዲ ያስገድደዋል። እንዳለመታደል ሆኖ ግን የአላህ አመስጋኝ ባሮቹ ትንሽ ሆነው በፀጋው የሚክዱት በዙ!

አላህ ከጥቂት ባሮቹ ያድርገን!...ምክንያቱም አመስጋኝ ባሮቹ ጥቂት ናቸውና!
➙ መልካም የጁሙኣ ግዜ ይሁንልን።
ISLAMINDSET

የአረብ ገንዳ መስጂድ ወጣቶች

31 Jul, 17:51


ገንዘብ ሲገኝ ሊያስደስት ይችል ይሆናል። ያስደስት እንጂ የውስጥን እርካታና መረጋጋትን በፍፁም አይሰጥ።ለዛ ነው ገንዘብ የሌላቸው ሰዎች ገንዘብን ሲያገኙ በፊት ላይ ከነበሩበት አላህ የሚወደው ቦታ የምናጣቻው። ገንዘብ ያላቸው ከሌላቸው ሰዎች ይበልጥ ሩጫ እና ጭንቀት ውስጥ ይገባሉ።አላህ ያዘነላቸው ሰዎች ሲቀሩ!...እንዲሁ ገንዘብ ሲታጣ ሊጠብ እና ሊያጨናንቅ ይችል ይሆናል። ነገር ግን አያስደነግጥም። ምክንያቱም መታጣቱ ቋሚ አይደለም።ግዜውን ጠብቆ ይመጣል። በነዚህ በሁለቱ ተቃራኒ ጎኖች አንድ ሙዕሚን ገንዘብን ሲያገኝ የሁሉ የበላይ እንደሆነ አያስብም...ሲያጣም ከሁሉ የበታች እንደሆነም አይሰማውም። ሙስሊም ገንዘብ ሲያገኝ ሆነ ሲያጣ አንድ አይነት ባህሪ ብቻ ነው ያለው... እሱም በአላህ ፈተና ላይ እንደሆነ ያስተነትናል።
ISLAMINDSET