እውነት ለሁሉ @kettegawa_ewnet Channel on Telegram

እውነት ለሁሉ

@kettegawa_ewnet


በዚ ሁሉም ነገር አላፊ በሆነው ዓለም ውስጥ እየኖርን ፣ ለማያልፈው ዘላለማዊ ለሆነው ለክርስቶስ እንኑር "እርሱ ብቻ የማይሞት ነውና" (1ኛ ጢሞ 6፡16)

እውነት ለሁሉ (Amharic)

እውነት ለሁሉ (Truth for Everyone) በእያንዳንዱን ሰነፍ እና ወንድማችን በማንኛውም መስማት በሚል መምህር ታሪክ፣ ታክተኛ፣ ከሌላ በኋላ ዘር፣ ከእንጀራ፣ ፍወሪ፣ ፍለጋ፣ ትናጊ ወይም ፍርድ የመሆኑን ስለዚህ ከተማ ስለዚያ መድሃኒቱን ለመከላከል እና ለጭንቅናና ውድ ህግማን ለማየት እንዲለው የዚህ ቻንኦሉን ይመችልናቸዋል።nአጭር እና ማገዱ በተመሳሳይ ፈቃድ እና ጥያቄ ተጨማሪ እውነት ለሁሉ፣ ከዚህ ቻንኦሉ አንድ የይሞታ እና ትምህርት ቤት ሲሆን በዚህ ቻንኦሉ የመሳሪያ ቦታ ተቀባይነትን ተጠቅመን ከሚለው የቻንኦሊን አስተማሪ መምህራን ውስጥ ያለውን አትሌት ለመገንዘብ እና ለማስጠበቅ የእዚህ ቻንኦሉ አንድ የትናንታው አስተዳደር ተቀላቅለው።

እውነት ለሁሉ

17 Feb, 20:15


ክርስትያን የሚለው ስም የተሰጠን የት እንደሆነ 🙏❤️

ክርስትያን የሚለው ስም ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠን በሶርያ አንጾኪያ ነው፡፡

ሐዋርያት በዚያ ከተማ በስፋት ወንጌልን ያስተምሩ ስለነበር ሕዝቡ የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታዮች መሆናቸውን ሲያውቁ “ክርስቲያን” አሏቸው።

“ክርስቲያን” ማለት “የክርስቶስ ተከታይ” ወይም “የክርስቶስ ወገን” ማለት ነው። ስያሜው የተሰጠን የእምነታችን ማዕከልና መሪ የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን በመከተላችን ነው።

በሐዋርያት ሥራ 11:26 ላይ እንዲህ ይላል፡- “በአንጾኪያም ደቀ መዛሙርት መጀመሪያ ክርስቲያን ተባሉ።”

በተጨማሪም፣ 1 ጴጥሮስ 4:16 ላይ “ክርስቲያን ስለ መሆኑ ግን ቢሰቃይ አይፈር፤ ይልቁንስ በዚህ ስም እግዚአብሔርን ያክብር።” ይላል።

ስለዚህ፣ ክርስቲያን የተባልነው የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይ በመሆናችን ነው፣ ይህንንም ስም ያገኘነው በአንጾኪያ ነው።🙏❤️

እውነት ለሁሉ

15 Feb, 20:02


only Jesus አማኞች በራሳችሁ ፈትታችሁ ከምትጠቅሷቸው ጥቅሶች ሌላ አንድ አካል እንደሆኑ ሚገልጽ ቃል ይኖራችሁ ይሆን? ምክንያቱም እስከ አሁን አንድ አካል እንደሆኑ ሚገልጽ ጥቅስ ስለሌለ

እውነት ለሁሉ

15 Feb, 19:54


ዩሀ14:14 ላይ ማናቸውም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አረገዋለው ብሎ ቁጥር 15 ላይ እኔ አብን ለምናለሁ ያለው አብ ካልሆነ ማናቸውን ነገር በስሜ ልምኑ ያለው አምላክ ይለምናል

ከጅምሩ የራሱን ግምት ተናገረ እንጂ ሁለት አካል መሆናቸውን ሚያፈርስ ንግግር አደለም ኢየሱስ ለምኖ ሚሰጠን ነው አልተባለም አንልምም በስጋው ወራት የተናገረውን ዘለአለም እንደሚለምን አርጎ መናገር ከማንምጋ ሳይሆን ከመጽሀፍ ቅዱስ ጋ ነው ሚያጋጫው
fore example በሰዶምና ገሞራ ምክንያት እግዚአብሔር ተጸጸተ ሚል ቃል አለ ቃሉን ቀጥታ ባንጠራውም በዛች ሰአት የተነገረውን ሁሌ አሁንም እንደሚል አርገን እንጠቀመዋለን? አንጠቀመውም ኢየሱስ ሰውም አምላክ በመሆኑና ልመናው የቤዛነቱ አንድ አካል ስለሆነ ተናገረ
ስለዚህ እኔ ወደ አብ እሄዳለው ብሎ ኢየሱስ ወደ አብ ሚሄድ ሌላ ሁለት ማንነት መሆናቸውን ሚያፈርስ ምንም ነገር አይኖርም ለመልስም ተብሎ የተቀረበው የማይሆን ጠማማነት መልስ ነው እኔ አብን ለምናለሁ እያለ የሚለመንና የማይለመን አካል መኖሩን በደብ እያሳወቀ አንድ አካል ናቸው ማለት ጭፍንነት ነው አካልነት ጨርሱና ስጋዌ ላይ ትገባላችሁ ሲጀመርም አካልነት ላለመቀበል እንዴት ምናምን ተብሎ እኔ በማስበው መንገድ ልቀበል ማለት ትልቅ ስህተትም ጭምር ነው የተገለጠውን አሜን ብለን እንቀበላለን እንጂ
ቁጥር 23 ላይ ወደ ርሱ እንመጣለን የተባሉት አብና ወልድ ነው አብ እንዴት ይመጣል ስለዚህ አንድ አካል ናቸው ?
እሄ አስተሳሰብ መጽሀፍ የዘነጋ በራሱ መንገድ የሚጓዝ ሰው ሚናገረው ነው only Jesus አማኞችም በራሳቸው መንገድ ሚጓዙ ስለሆኑ ነው የተናገሩት ዘፍ 11:7 ላይ ኑ እንውረድ ብሎ ሲናገር እግዚአብሔር ከቦታ ወደ ቦታ ሚንቀሳቀስ ሴለሆነ ነው? ከመጽሃፍ ቅዱስ ርቆ በራሱ አለም ሚዞር እንዲ ነው ስለዚህ 14:23 ወደ ርሱ እንመጣለን የተባለው ምንም ሁለት አካልነታቸውን እንዳልሆኑ ሚያስረዳ አደለም። መንፈስ ቅዱስስ እነሱ ከሄዱ በኃላ ነው ሚመጣው? እስቲ እንደው ታዘቡ እሄ ጥያቄ ኢየሱስና አብ ሁለት አካል አለመሆናቸውን እንዴት ነው ሚያሳይለት መንፈስ ቅዱስስ ማለቱ ? እንደ በቀቀን አታደጋግሙን በመለኮት አንድ ስለሆኑ መለኮታዊ ስራን ሁሉም በአንድ እንደሚሰሩ የታመነ ስለሆነ ባታደጋግሙን

ቁጥር 26 አብ በስሜ ሚልከው መንፈስ ቅዱስ ብሎ የተለያየ ማንነቶችን ሚገልጸውን ጥቅስ አንድ ገጽ ገልብጥ አለኝ 15:26 እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ ይላል ኢየሱስ አብ ካልሆነ እንዴት መንፈስ ቅዱስን ይልካል?
የኛን ሀሳብ ምንም ሳይረዳ በግምት የጻፈ መሆኑን እሄ ጥያቄ ያሳያል መንፈስ ቅዱስ ሚልክ አምላክ ነው ኢየሱስም መንፈስ ቅዱስን ይልካል ከአብጋ አንድ መለኮት ስላለው። ስለዚህ  ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስን መላኩን እንደዛ ብለን በመጽሀፉ መሠረት እንረዳለን ኢየሱስ መንፈስ ቅዱስን መላኩ አንድ አካልናቸው ሚል ሀሳብ የለውም
ቁጥር 26 አብ በስሜ ሚልከው መንፈስ ቅዱስ በማለት ከአብ ነጥሎት በአካል ሲናገር ነበር ስለዚህ አንድ አካል ለማለት ምንም አሳማኝ ነገር የለውም

በመላክም አንድ ናቸው ? አለ አዎ መንፈስ ቅዱስን ሚልክ በብሉይ ኪዳን አምላክ ብቻ ነው ኢየሱስም ከአብጋ በመለኮት አንድ ስለሆኑ ኢየሱስም ሊልክ ይችላል ይህ ሥላሴን ትምህርት በግልጽ የሚያሳይ ነው
በሐዋ2:1 ላይ የወረደውን ማን ነው የላከው? እሄ  ጥያቄ ማንኛውም አካል ቢልከው የሥላሴን አካልነት አደለም የሚያስብል አደለም በመለኮት አንድ ስለሆኑም አብ ላከው ሲል ወልድ አልላከም ማለት አደለም የወልድም ፍቃድ ነውና በፍቃድ በመለኮታዊ ስራ አንድ ስለሆኑ
አብ ከሆነ የላከው የወልድ መቼ ነው? ከጅምሩ የተባለሸ ጥያቄ የአብ መንፈስ ሌላ የወልድ መንፈስ ቅዱስ ሌላ አይልም አብ ላከው ሲባልም የወልድም ፍቃድ ነው በመለኮታዊ ስራ በመገናዘብ አንድ ስለሆኑ

እኛ በወልድ ውስጥ አብ ይኖራል ይኖራል ከተባለ ደግሞ አንድ አካል ናቸው ?
አልክ እንጂ አንድ አካል መሆናቸውን ሚገልጽ ማስረጃ የለም በኔ የሚኖረው አብ ብሎ ስራ በማለት ስራን በመለኮታዊነት እንደሆነ በኔ ይኖራል ያለው እዛው ላይ አሳየን
በእኔ የሚኖረው አብ ብሎ ሌላ አካልን እየጠራ ነው አንድ አካል ከሆነ በእኔ የምኖረው አብ እኔ ለምን አላለም ምክንያቱም አንድ አካል ሳይሆን ሥላሴ ሁለት ማንነቶች ስለሆኑ እናንተ ግን በባዶ ነው በእኔ የምኖረው እኔ ብሎ ለምን አልተናገረም በእኔ የሚኖረው አብ ብሎ ለምን አብን መጥራት አስፈለገ ምክንያቱም በስራ በመለኮንትነት እንጂ በአንድ አካል ስላልሆኑ

መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ውስጥ የሚኖረው የተባለው ሐዋርያት አንድ አንድ አካል መንፈስ ቅዱስጋ ስለሆኑ ነው ? አደለም ለምን መኖር ሚለው ስራን እንጂ አንድ አካልነትን ስላልሆነ በደፈናው ኢ መጽሀፍ ቅዱሳዊ አስተምህሮ ተቀበሉ አይባልም የቀረህ እንዳልከው ትምህርታችሁ ሚደግፉ ያላችሀቸው ጥቅሶች አንድ ነው የቀረው አንተም እንዳልከው በእሱም መለሳለሁ

እውነት ለሁሉ

14 Feb, 17:19


Galatians 1:1Pray for all the saints. Pray also for kings, 1 Timothy 2:2 and potentates, and princes, and for those that persecute and hate you, Matthew 5:44 and for the enemies of the cross, that your fruit may be manifest to all, and that you may be perfect in Him.
Epistle of Polycarp to the Philippians 12

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በቅዳሴዋ እንደምጸልየው

እውነት ለሁሉ

14 Feb, 13:13


የወልድ አምላካዊ ባሕርይ ከሥጋ ባሕርይ ጋር ተዋሕዶ አንድ ባሕርይ ከኾነ ሥላሴ በባሕርይ አንድ ናቸውና ሥላሴ ሰው ኾኑ አያስብልምን?

ይህ ጥያቄ በ5ኛው እና በ6ኛው ክፍለ ዘመን በኬልኬዶናውያን እና በኢኬልቄዶናውያን መካከል በተደጋጋሚ የሚነሳ የተዋሥኦ ርእስ ነበር። ኬልቄዶናውያን (የአሁኑ Eastern Orthodox )የሥላሴ አምላካዊ ባሕርይ ከሰውነት ባሕርይ ጋር ድንበራቸውን ጠብቀው በክርስቶስ አካል ውስጥ በመሐዋዳቸው ክርስቶስ በአምላካዊ የተለየ አካሉ ኹለቱን ባሕርያት ይዟል ሲሉ ኢኬልቄዶናውያን (የአሁኑ Oriental Orthodox) ደግሞ  የክርስቶስ ባሕርይ ከኹለት የኾነ አንድ እንጂ በኹለትነት አልቀጠለም በማለታቸው ኬልቄዶናውያን የሥላሴ ባሕርይ በምልዓት ሰው ኾኗል ብለው ያምናሉ በማለት ያሙአቸው ነበር።

ይህን ጥያቄ ለመመለስ ከኢኬቄዶናውያን ወገን እስክንድርያዊው ዮሐንስ ተአቃቢ (John Philoponus) ጥረት አድርጓል። ነገር ግን ዮሐንስ ተአቃቢ ክርስቲያን ከመኾኑ በፊት ፈላስፋ ነበርና ጥያቄውን የመለሰበት ኹኔታ ፍልስፍናው ተጽእኖ አድርጎበት ወደ ስህተት ገባ። እንደ ዮሐንስ ተአቃቢ ሃሳብ አንድ ባሕርይ (Ousia) ከparticularity (Hypostasis) ውጪ ሕልውና (existence) የለውም  ለምሳሌ ድንጋይነት የሚባል ባሕርይ ከአንድ ፊት ለፊቴ ካለ ድንጋይ ውጪ በሕልውና የለም ስለዚህም ይህ ድንጋይነት ባሕርይ ሕልው ኾኖ ያለው በዚህ ፊት ለፊቴ ባለው ድንጋይ ብቻ ነው ማለት ነው ይህ ሃሳብ በፍልስፍና አጠራር nominalism ይባላል። ዮሐንስም ይህን የፍልስፍና ሃሳቡን ሥላሴ ላይ ተጠቀመበት በሥላሴ ዘንድ ደግሞ 3 particularity ነው ያለው እርሱ ደግሞ አንዱ ባሕርይ ከparticular ውጪ ሕልውና የለውም ብሎ ስለሚያምን እያንዳንዱ የሥላሴ አካል የየራሱ ባሕርይ ሊኖረው ይገባል በማለት ደመደመ። ስለዚህም ወልድም ሰው ሲኾን ከአብ እና ከመንፈስ ቅዱስ የተለየ ባሕርይ ይዞ ሰው ስለኾነ አብ እና መንፈስ ቅዱስ ሰው አልኾኑም በማለት የኬልቄዶናውያንን ጥያቄ መለሰ።

ቤተክርስቲያናችን ግን ይህን የዮሐንስ ተአቃቢ ሃሳብ ታወግዛለች ክርስቶስ ኹለት ባሕርይ አለው የሚለውን ም*ን*ፍ*ቅና ለመራቅ 3 መለኮት ወደሚል  ም*ን*ፍ*ቅና ገብቷልና። ታድያ ቤተክርስቲያናችን የኬቄዶናውያኑን ጥያቄ እንዴት ትመልሳለች? ይህን ጥያቄ በቤተክርሲያናችን ከቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ በኋላ ታላቅ የአንድ ባሕርይ ተዋሕዶ ጠበቃ የኾነው ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ (St. Severus of Antioch) መልሶታል። እንደ ቅዱስ ሳዊሮስ ገለጻ አንድ ባሕርይ (Ousia) በሕልውና የሚታየው በparticularity ቢኾንም በዛ በአንድ particularity ብቻ ሕልው የሚኾን አይደለም ለምሳሌ የአንድ ድንጋይነት ባሕርይ በተለያዩ ቦታ ያሉ ድንጋዮች ሊጋሩት ይችላሉ ልክ የሰው ኹሉ ባሕርይ አንድ እንደኾነ። የሥላሴ አምላካዊ ባሕርይው በየአንዳንዱ particularity ውስጥ ያለ መከፋፈል ሕልው ነው ነው እንጂ እያንዳንዱ አካል የየራሱ Ousia ሊኖረው ግድ አይደለም  ነገር ግን እያንዳንዱ አካል በOuisa ሕልው ነውና የየራሱ Hypostasis አለው። ወልድም ሰው ሲኾን በHypostasis (particularity) ደረጃ አንጂ በOusia (Generality) ደረጃ ስላልኾነ ሥላሴ ሰው ኾኑ አያስብልም። ነገር ግን ኬልቄዶናውያን እንደሚሉት አንዱ የክርስቶስ አካል ውስጥ የኹለት ባሕርይ (Ousia) ተዋሕዶ ካለ የሰው ባሕርይ በሙሉ ከሥላሴ ባሕርይ ጋር ተዋሕዷል ያስብላል (ይህ ሰው ኹሉ አምላክ ኾነ ማለት ነው።) በማለት በGenerality እና particularity መካከል ያለውን መስመር ባለማስመራቸው መሳታቸውን ያስረዳቸዋል።

{ኪዳን ዘኢየሱስ እንደጻፈው}

እውነት ለሁሉ

14 Feb, 05:03


Valentines day የወጣቶች የዳንኪራ ወጥመድ ዛሬ ተሰበረ። ዛሬ ማለትም አርብ ጌታችን ኢየሱስ አለምን ያፈቀረበት ፍቅሩንም እስከ መስቀል ሞት ገልጾ ያሳየበት ቀን ነው፣ ያለ ስስት ያፈቀረን እስከ መስቀል ሞት ለወደደን ለታላቁ አፍቃሪያችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የፍቅር መከራ ቀን በሰላም አደረሳችሁ።

     ወሰላሙ አለይኩም🙌

እውነት ለሁሉ

13 Feb, 09:12


ከገድላት ጋር በተያያዘ ብዙ ሰዎች የተዛባ አመለካከት ስላላችሁ pleas ነገሮች በቀስታ ለማየት ሞክሩ ትክክለኛ ገድላት ላነበባቸው ለተጠቀመባቸው ጥሩ ነው የሚያገኘውና የሚጠቀመው ነገር ይኖራል፣ ነገር ግን እያንዳንዱ ገድል ላይ የተጻፈውን ካላመንክ አንተ ክርስቲያን አይደለህም፣መናፍቅ ወዘተ የምትሉ አድቡ አንድ ነገር ልንገራችሁ እንኳን እናንተ ቤተክርስቲያንም ገድላቶቿን ለይታ አላስቀመጠችም አይደለም ተቀበሉ ማለቱ ቀርቶ፣ ለማንኛውም ግን ገድላት ክርስቲያን ወይም መናፍቅ የመሆን (ክራይቴሪያ) አይደሉም።

እውነት ለሁሉ

13 Feb, 07:27


🚩 መንፈስ ቅዱስ

መንፈስ ቅዱስ:- ከአብ ጋር አንድ መለኮት የሆነው አምላካችን! https://t.me/TheTriune/908

መንፈስ ቅዱስ አምላክ አይደለምን? ለወሒድ ዑመር የተሰጠ መልስ (ክፍል 1) https://t.me/TheTriune/1080

መንፈስ ቅዱስ አምላክ አይደለምን? ለወሒድ ዑመር የተሰጠ መልስ (ክፍል 2) https://t.me/TheTriune/1084

መንፈስ ቅዱስ በነጠላዊያን ዘንድ ማነው? https://t.me/TheTriune/1062

መንፈስ ቅዱስ አካል እንደ ሆነ ብሉይ ኪዳን አያስተምርምን? https://t.me/TheTriune/586

♦️ መንፈስ ቅዱስ በFather Kappes https://answeringislamblog.wordpress.com/2021/10/03/holy-spirit-worshiped-as-god/

እውነት ለሁሉ

12 Feb, 19:58


እመቤታችንን በተመለከተ

እመቤታችን እኛ ክርስቲያኖች እጅጉኑ አብዝተን እንወዳታለን ቤተክርስቲያን ለእመቤታችን ታላቅ ቦታ አላት ይህንንም በተለያዩ መጻህፍቶቿ የተገለጡ ናቸው፣ እንደሚታወቀው ቤተክርስቲያን አለማቀፋዊት እንደመሆኗ መጠን በአለም ውስጥ አለች ታድያ በዚህ ውስጥ ብዙ አባቶች ፈልቀዋል፣ እናም ስለ እመቤታችን በተለያዩ ድርሰቶቻቸውም ይሁን ስብከቶቻቸው የተለያየ ነገር አስቀምጠዋል።

እንዳልኩት የኢትዮጲያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ስለ እመቤታችን ያላት ክብር ተቆጥሮ አያልቅም ይህንን ስል ግን ሌሎቹ እህት አብያተክርስቲያናት አያከብሯትም እያልኩኝ አይደለም ለምሳሌ ኤፍሬም ሶርያዊው ስለ እመቤታችን ብዙ ነገር ብሏል ቅዱስ ያዕቆብ ዘስሩቅ ሌሎችም አሉ በጣም ብዙ ነገር ያሉ ይህ እንዳለ ሆኖ ግን ሌሎችም አበው አሉንና እነሱስ ምን አሉ ብለን ብንጠይቅና ሪሰርች ነገር ብናደር ብዙ ነገር እናገኛለን፣ አንዱ አባት ያለው ሌላኛው አባት ላይቀበለው ይችላል ሌላኛው ያለውን ሊቀበለው ይችል ይሆናል ተቃራኒ የሚመስሉ ነገሮች ይናገራሉ ካላቸው መረዳት አንጻርና ከሚያውቁት ነገር የተነሳ personal view ያስቀምጣሉ።

(Original ኃጢአት) የሚባለው ነገር ላይ ብዙዎች ብዙ ነገር ብለዋል ሰሞኑም ብዙ ነገር እየተነገረና መጻህፍት እየተገለጡ ነው ትንሽ አለመግባባትም ነገር አለ ይህ እንዳለ ሆኖ ግን ሁለት የሚቀርቡ ሀሳቦች ይኖራሉ ቀርበውማል እርሱም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም (የአዳም ባህሪ፣መርገም የገጠመው ስጋ) ይዛለች ወይስ አልያዘችም? በሚለው ህሳቦቶች ላይ ይዛለች እና አልያዘችም የሚሉ ሁለት ሀሳቦች ተነስተዋል ለእነዚህ ህሳቦቶችም አባቶች ሊቃውንት ተጠቅሰዋል፣ እንዲህም ሆኖ ግን ሁለቱምህሳቤዎች ላይ የሆነ ነገር ከመያዝ ይልቅ መተቻቸት አንዱን አንዱ መናፍቅ የማለት ነገር አለ ይመስለኛል ከእመቤታችን ፍቅር የተነሳና ካሉት ሊቃውንት ፅህፈቶች የተነሳ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገር ያለ በሚመስልም መንገድ ይመስላል ብቻ ጌታ ያውቃል እንዲህ ያሉ ነገሮች አሉ።

የሆነው ሆኖ ይህ ነገር እንዴት ይታያል ለሚለው ነገር personal view ላስቀምጥ፣ እንደምናውቀው የሰው ልጅ በመበደሉ ምክንያት ከእግዚአብሔር ፀጋ ተለይቶ ነበር ከዚህም የተነሳ የሰው ልጅ ዳግም ወደ እግዚአብሔር ጸጋ ለመመለስ ታላቅ የማይገፋ ተራራ ሆኖበት ነበር ስለዚህም አምላክ ሰው መሆንን ወደደ ሰው ለመሆን ደግሞ መወለድ ያስፈልጋልና ይወለድባት (ያድርባት) ዘንድ አንዲትን ሴት መረጠ እርሷም ቅድስት ድንግል ማርያም ነች፣ የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ አብ ከሴት የተወለደ ልጁን ላከልን እርሱም ከእርሷ በነሳው ሥጋ መስዋዕትን አቅርቦ ኃጢአታችንን በመስቀል ላይ አነጻው እንዲህ ነው በአጭሩ።

አሁን ይህንን ከያዝን እመቤታችንስ ከዚህ ሰው ዘር ከገጠመው የጸጋ መራራቅን አግኝቷታል፣ (ከውድቀት በኋላ ያለውን የአዳምን ሥጋ ነው የያዘቺው)? ወይስ የመጀመሪያውን ምንም ውድቀት ያልገጠመውን (ውድቀት ያልገጠመውን ሥጋ)? ይህንን በሁለት view እንየው ከዛን የእናንተ ድምዳሜ ለእናንተ ልተወው። እኔ ብቻ ከተማርኳቸው ልጥቀስላችሁ!!

(Original ኃጢአት) ከእመቤታችን ጋር በተያያዘ የኢትዮጲያ ሊቃውንት ምን አሉ፣ሊቁ አባ ህርያቆስ በቅዳሴ ማርያም ድርሰቱ “የባህርዩ ርቀትና ጥልቀት የማይመረመር አማኑኤል መርገም ያልወደቀበትን ፡ንፅህ ጠባይ ፡ ቅድስትና ባህርይ ያላደፈባትን ከአዳም ጥንት ባህርይ የተገኘ ያንቺን ስጋና ነፍስ ተዋሐደ”
ሊቃውንት መተርጉማን አባ ህርያቆስ “ዘእምጥንተ ስጋሁ ለአዳም” ያለውን ሲተረጉሙ ህገ እግዚአብሔርን ባለመጠበቁና ፈቃደ እግዚአብሄርን በመተላላፉ ምክንያት ብልየት (ዕድፈትና ርኩሰት) አግኝቶት የነበረ የሰው ባህርይ ተአዛዚተ እግዚአብሔር በሆነችው በእመቤታችን  በድንግል ማርያም  ባህርይ ነፅቶ ተገኘ ማለት ነው ብለዋል፡፡
ይህም ትርጓሜ ሊቁ ቅዱስ ያሬድ “ማርያምሰ ተሐቱ ውስተ ከርሡ ለአዳም ከመባህርይ ፀአዳ (ድንግል ማርያም ግን በአዳም ባህርይ ውስጥ እንደንፁህ እንቁ ታበራ ነበር ) መፅሃፈ ድጓ ገፅ 94 ሲል ከተናገረው ኅይለ ቃል ጋር በምስጢር የተገናዘበና የተሰናሰለም ነው ይላሉ ፤ ይህም ምስጢሩ ምንም እንኳን እመቤታችን ከአዳም ባህርይ የተገኘች ዘርዐ አዳም ብትሆንም ቅሉ የአዳም ገንዘብ  የሆነው የሓጢአት ዝገት ከፅርየቷ (ከንፅሀ ጠባይዋ ፡ ከቅድስና ባህርይዋ) አላሳደፋትም ፤ ምክንያቱም የዕንቁን ባህርይ የተገኘበት ቦታ ፅርየቱን አይለውጠውምና ነው ይላሉ፡፡

ቅዱስ ያእቆብ ዘስሩግም (የእግዚአብሄር እናት) በሚለው ስብከቱ (ድርሰቱ) ላይ “ከላይ ከገለጥነው አማናዊ ትምህርት ውጭ ግን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአዳም መርገም (ጥንተ አብሶ) ነበረባት ማለት ቃለ መፃህፍትን ማስተሐቀርና ማሳበልም ነው" በማለት ያስቀምጣሉ።  

ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም በአርጋኖን መጽሐፋቸው “አደፍ ጉድፍ የሌለብሽ ንፅህት ሆይ ያለሐጢአት ፅሪት ፡ ያለርኩሰትም ቅድስት ሆይ የድንግልናሽ ምስጋና እፁብ ድንቅ ነው ፤ የንፅህናሽም ውዳሴ የተደነቀ ነው፣ስለዚህም ክብርሽን ገናንነትሽን ልንናገር ይገባናል፡፡ በነቢያት መፃሕፍት ከዳዊት ዘር ከወገኖቹም ነገድ ክርስቶስ እንዲወለድ ተፅፏል ፤ እንኪያ በሄሮድስ ልጅ አላደረም፣ከይሁዳም አለቆች ባንዱ ልጅ፣ ነገር ግን ከገሊላ ልጆች ለእናትነት የምትበቃ አላገኝም፣ ስለዚህም ድንግል ሆይ፣አንቺን በትህትና በድንግልና ተጠብቀሽ የምትኖሪይቱን ብላቴና ወደደ፣ለመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ የሚሆነው አዳራሽ ንፁሁን ስጋሽን አገኝ" በማለት ያስቀምጣሉ።

እንግዲህ እኛ ምን እንላለን እግዚአብሔር አምላክን ከማመስገን ውጪ እነዚህን የመሳሰሉ ሊቃውንት ሰጥቶናል ሎል አሁን ደግሞ እስኪ አንድ አባት ልጥቀስላችሁ እመቤታችን ከአዳም የተለየ ነገርን አልያዘችም ለሚለው ሀሳብ፣ አንድ ያልኩት አንድ ብቻ ኖሮ ሳይሆን ነገሮችን ለማሳጠር ያህል ነው አልያም ስማቸውን ብቻ አስቀምጥላችሁ እና እያመጣን እንማማርበታለን።

Eve having become disobedient, was made the cause of death, both to herself and to the entire human race ; so also did Mary, by yielding obedience, become the cause of salvation, both to herself and the whole human race ( St Ireanus of Lyon, Against Heresies Book 3, Chapter 22, 4)

በአጭሩ የሰው ዘር በአጠቃላይ በኃጢአት መውደቁን ይናገርና ሔዋን አለታዘዝም ስትል የብዙዎች የሞት ምክንያት ስትሆን (እመቤታችንም በመታዘዞ እሺ በማለቷ ምክንያት ለራሷም ለብዙዎችም የመዳን ምክንያት ሆነች) በማለት ይናገራል።

ሌሎችንም መጥቀስ ይቻላል እነ (አትናቲዎስ፣ የኢየሩሳሌሙ ቅዱስ ቄርሎስ) እነዚህንም መጥቀስ ይቻላል አዳማዊነትን በመያዟ ምክንያት እርሷንም እንዳዳናት አይነት ነገር ወዘተ የሚናገሩትን፣ ለማሳጠር ያህል ግን ይህንን ይበቃል።

ሙግት አንድ፣ ከላይ የተጠቀሱት ሊቃውንት ከምን አንጻር ተናገሩ?

ሁለት፣ ንጹህ ነሽ ማለት ከግብር ኃጢአት. ጋር በተያያዘ ወይስ ከአዳማዊነት ጋር በተገናኘ?

ሦስት፣ የሰው ዘር በውድቀት ምክንያት በትንሳኤ በኩል መነሳትን ካስፈለገው፣ እመቤታችንም ትንሳኤን አግኝታለችና የወደቀውን አዳማዊነት ካልያዘች ትንሳኤ ማግኘቷ ለምንድን?

እያሉ የሚቀርቡ ሙግቶች አሉ፣ሁለቱም ሀሳቦች ግን አያስተቻችም።

   {ወሰላሙ አለይኩም}።

እውነት ለሁሉ

12 Feb, 11:48


John 14 አማ - ዮሐንስ
1: ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።
እሄንን ጥቅስ ማያጣሙበት ብዙ መሰናክሎች አሉ በተቃራኒው ሁለት ማንነቶች ብለው እንዲያምኑ በብዙ አይነት እንደማያስኬዳቸው እና እንደማያወጣቸው እናየለን ከጅምሩም ቃሉን አያሳይም ብለው ባይመልሱም

ይህን ጥቅስ ሁለት ሊታመኑ ሚገቡ ማንነቶች እንዳሉ ይገልጻል ለተባለው መልስ አንድነታቸው የሚያሳይ ጥቅስ ዘሎ ዩሀ12:45 ላይ ነው የሄደው ግን መነበብ ያለበት ከቁጥር 44 ጀምሮ ነው ቁጥር 44 ጀምሮ በኢየሱስ በማመን በአብም ማመን እንደሆነ እየገለጸ ነው 45 ሚናገረው
እዚጋ ሊታወቅ ሚገባ ነገር አለ እሱም አብና ሁለት ማንነቶች ቢሆኑ አንድነት የሌላቸውም አላልንም አንድነት አላቸው ሚለያየን ይሄ አንድነት only Jesus አማኞች አንድ አካልነትን ሲሉ እኛ ሥላሴ አማኞች ደሞ በመገናዘብ በመለኮት በስራ በስልጣን ሌላም ሌላም እንላለን

ዩሀ14:1ን ሁለት ማንነቶች ሚታመኑ እንዳሉ ይጠቅሳል ለሚለው መልስ ዩሀ12:45 እና ተመሳሳይ ጥቅሶች አንድ አካል ናቸው ለማለት ስለምትጠቅሱ አንድ አካልነት አያሳይም በማለት ዩሀ14:1ን ጠቀስን ስለዚህ ዘሎ የአንድነት ጥቅስ ላይ መሮጥ መልስ አይሆንም ከመጀመሪያውኑ የአንድነት ጥቅሶችን በመጥቀስ አንድ አካል ስለምትሉን አንድ አካልነትን አያሳይም በሌላም ክፍሎች ሁለት ማንነቶች አሉ ብለን የጠቀስነው ስለሆነ መልሶ የአንድነት ጥቅሶችን መጥቀስ circular ጨዋታ መዟዟር እዛው እዛው እንጂ መልስ አደለም። ሀሉት ማንነቶች ለሚገልጽ ጥቅስ መልስ የአንድነት መጥቀስ ሁለቱን አስታርቆ አለመቀበል አንዱ ላይ መለጠፍ እና መሟጨጭን ነው ሚያሳየው ።

ለእኛ እንደሚደግፍ የጠቀሱት ማየት ይቻላል ለብቻዬ የፈጠርኩ ሚሉ ጥቅሶችን በመጥቀስ የተለያየ አካላት ቢሆኑ እንዴት ብቻዬን አለ ሥላሴ አደለም በማለት ሲጠይቁ የእኛም መልስ በመለኮት አንድ ስለሆኑ ፈጣሪ ብቻውን የፈጠረ ብለን እንጂ የፈጠሩ ብዙ አምላኮች ብለን አናምንም ስለዚህ በመፍጠር አንዱ ፈጣሪ ፈጠረ ይባላል። እንደዚ ሲባል ግን ሌሎች ማንነቶች የሥላሴን ተነጥሎ አደለም አብ ፈጠረ ሲባል ወልድ ተለይቶ አደለም በማለት ምንመልሰውን በኢየሱስ አመነ ሲባል ከአብ ተነጥሎ በኢየሱስ ብቻ ማመን አደለም በአብም ማመን ነው በመለኮት ስልጣን አንድ ስለሆኑ በኢየሱስ ማመኑ በአብም ማመኑ ነው ምንለውን የስላሴ ትምህርት ሚደግፍ ነው የጠቀሱት ከቁጥር 44 ጀምሮ  የእኛን ትምህርት ሚያስረዳ ነው
John 12 አማ - ዮሐንስ
44: ኢየሱስም ጮኸ፥ እንዲህም አለ፦ “በእኔ የሚያምን በላከኝ ማመኑ ነው እንጂ በእኔ አይደለም፤
45: እኔንም የሚያይ የላከኝን ያያል።


📖በማለት ኢየሱስን ማየት አብን ማየት እንደሆነ ኢየሱስ ከአብ የተለየ መለኮት ስላልሆነ በኢየሱስ ማመንም በአብም ማመኑ እንጂ በመለኮት እንደሚለያዩ በኢየሱስ ብቻ ማመኑ አደለም ብሎ ኢየሱስ እንደተናገረው only Jesus ወንድማችን መልስ ብሎ ብሎ  የተናገረው ዩሀ12:44-45
እኛ የምንለውን አስተምህሮ ሚደግፍ ነዉ (የጠቀሱት ዩሀ12:44-45


እንደዛ አደለም ብለው አንድ አካል ስለሆኑ በኢየሱስ አመነ ሲባል በአብም ነው ኢየሱስን ማየት አብንም ማየት አንድ አካል ብለው ሚያምኑ የእኛን bold ያረግነበት እምነታችን ሚቃወሙ only Jesus አማኞች ጥያቄአችን
John 3 አማ - ዮሐንስ
18:  በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።

በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስላላመነ ብሎ ከአባቱ አብ ነጥሎ ልጁን እንዴት ሊጠራው ቻለ ታዳ ኢየሱስን ማየት አብን ማየት በኢየሱስ ማመን በአብም ማመን ነው በመለኮት በስልጣን ሳይሆን አንድ አካል ስለሆኑ ነው ብለው በሚያምኑት እምነታቸው መሠረት
John 3 አማ - ዮሐንስ
18: በማያምን ግን በአንዱ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ስላላመነ አሁን ተፈርዶበታል።

ለምን ታዳ ይሄን ጥቅስ አብን ነጥሎ በልጁ ያላመነ ይፈረድበታል ለምን ተባለ አንድ አካል ከሆኑ? እኛ በመለኮት አንድ ስለሆኑ በአካል ሁለት የተለያዩ ማንነቶች ስለሆኑ ብለን አዎ በልጁ ብሎ ከአባቱ ነጥሎ በአካሉ ጠርቶታል በመለኮት በስልጣን አንድ ስለሆኑ  የጠቀሳችሁልን ዩሀ12:44-45 ብለን እናምናለን
ከላይም እንደተገለጸው ግን አንድ አካል ብላችሁ በምታምኑበት መሠረት ግን ለምን ከአብ አባቱ ነጥሎ በልጁ ያላመነ ይፈረድበታል ለምን አለ የተለያየ አካል ካልሆኑ? ለዚ መልስ የአንድነትን ጥቅስ መጥቀስ ከሆነ አትድከሙ የአንድነት ጥቅሶችን አንድ አካል ስለምትሉን ስለሆነ የሁለት ማንነቶችን የጠየቅነው አትልፉ ምጠቅሷቸው ጥቅሶች አንድ አካልነትን ከሆነ ለምን በእግዚአብሔር ልጅ ብሎ ከአባቱ ነጥሎ መጥራት  ዩሀ13:18 ላይ አስፈለገ )?

በተጨማሪ ማጠቃለያ

John 14 አማ - ዮሐንስ
1: ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።

☝️እሄን biblical fact ሁለት ማንነትን አያሳይም ብላችሁ ከካዳችሁት በተመሳሳይ መልኩ
👇👇👇👇
Exodus 14 አማ - ዘጸአት
31: እስራኤልም እግዚአብሔር በግብፃውያን ላይ ያደረጋትን ታላቂቱን እጅ አዩ፥ ሕዝቡም እግዚአብሔርን ፈሩ፥ በእግዚአብሔርም በባሪያውም በሙሴ አመኑ።

በእግዚአብሔርም በሙሴ አመኑ ሚለው እግዚአብሔር እና ሙሴ አንድ አካል ስለሆኑ ነው?

ቃሉ ተመሳሳይ ነው ማየት ይቻላል
የሙሴ👇
Exodus 14 አማ - ዘጸአት
31:በእግዚአብሔርም በባሪያውም በሙሴ አመኑ።
የኢየሱስ 👇
John 14 አማ - ዮሐንስ
1:በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።

በእግዚአብሔር ማመን በኢየሱስም ማመን ተብሎ የተገለጸው
አንድ አካል ናቸው ብላችሁ ምታምኑ ከሆነ በተመሳሳይ ቃል በእግዚአብሔርም በሙሴ አሙኑ ሚለው ቃል ሙሴና እግዚአብሔር አንድ አካል ስለሆኑ ነው ያስብላል?

የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።

እውነት ለሁሉ

11 Feb, 18:52


ቅዱስ ቄርሎስ)

‹‹በቀናች ሃይማኖት አንድ ሁነው ከእርሱ ለሚቀበሉት ሰዎች ሁሉ ለይቅርታና ለምሕረት ፣ ለድኅነት እና ለረድኤት ለነፍስና ለሥጋ ሕይወት ይሁንላቸው። ለበደል ማስተሥርያ ለኃጢአት ይቅርታ ለትንሳኤ ሙታንና ለአዲስም ሕይወት ይሁንላቸው።››  (Anaphora Of St Cyril of Alexandria Number 75 & 74)

‹‹ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ ወደ ክርስቶስ ሥጋ እና ደም ተለውጧል። እናም እነዚህን (ሥጋና ደም) በመቀበል የክርስቶስን ሕይወት ሰጪ እና የቅድስና ተካፋይ ለመሆን እንመጣለን።›› (Commentary on the Gospel of Matthew 26,27)

እውነት ለሁሉ

11 Feb, 18:44


መንፈስቅዱስ ለአብ ምኑ ነው?

እውነት ለሁሉ

11 Feb, 17:20


የሐዲስ ኪዳን ጥምቀት መስራቹ ማነው?

እውነት ለሁሉ

11 Feb, 12:07


እነኋት እናትህ . . .የፍቅርን እናት ተሰጠችን
የእሾህ አክሊል ዘውድን ተቀዳጅቶ በጎልጎታ በመስቀል ላይ የነገሰው ፍቅር ጌታችን ኢየሱስ ስለ ሰው ልጅ ፍቅር እና መዳን በደም የተነከሩ፣ በደም የተጋረዱ ዓይኖቹን በእንባ ጎርፍ ወደምትታጠበው እናቱ ዞር አደረገና አያት፤ አንገቱንም ዘንበል አድርጎ በመከራና በሐዘን የጎበጠች እናቱን በፍቅር ዓይን በአንክሮ ተመለከታት… በዛ ጭንቅ ውስጥ በመስቀል ጣር ላይ ሆኖ እንኳን ጌታችን ቅድስት እናቱን አልዘነጋትም፣ አልተዋትም፡፡ አዎ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን እናቱን ይቅርና ለሚሳለቁበት፣ ለሚሰድቡትና በጦር ለወጉት እንኳን በመጨረሻ የመስቀል ላይ መከራው ሰዓት፡- ‹‹አባት ሆይ የሚሠሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው!›› ሲል ይቅርታንና ምሕረትን ነበር የማለደላቸው፣ በጎልጎታ በመስቀሉ ዘንድ ከልጇ ሥር እስከ መጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ ከልጇ ሳትለይ የቆየችው ይህች ምስኪን እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም አስቀድሞ በአረጋዊው ስምዖን እንደተተነበየላትና እንደተነገረላት፡- ‹‹ከክርስቶስ ኢየሱስ የተነሳ በነፍሷ የመከራ፣ የስደትና የጭንቀት ሰይፍ ያለፈባት ናት፡፡›› (ሉቃ 2:) በሄሮድስ ዘመን ገና በጌታ በሕጻንነቱ ወራት ከሄሮድስ የቁጣ ሰይፍ ለመሸሽ በግብጽ በረሃ የተሰደደች፣ የሕይወትን ራስ፣ የእስራኤልንና የአሕዛብን ሁሉ ተስፋ የሆነውን ጌታን ታቅፋ በሲና በረሃ የተንከራተተች፣ የተጠማች ፣ የተራበች፣ የተገፋች፣ የተጎሳቆለችና በብዙ ጭንቀት ውስጥ ያለፈች… እናም ገና ጌታን ከወለደችበት ወራት ጀምሮ በነፍሷ ባለፈው የሐዘን ሰይፍ የተነሳ በመከራ ደቃ፣ ሰውነቷ ገርጥቶ፣ አይኗ በእንባ ጎርፍ እየታጠበ ነፍሷ ተጨንቃ የሐዘን ከል ለብሳ በመስቀሉ ስር የተገኘቸውን እናቱን ልጇ ኢየሱስ ክርስቶስ በፍቅር ዓይን አያት፣ በፍቅር ዓይኑ ቃኛት፡፡ እኛንም በፍቅር ዓይኖቹ ይቃኘን!!

በዛ ሁሉ ጭንቀትና እንደ መርግ በከበደ መከራ ውስጥ በሐዘን የተጎሳቆለች በጌታችን እናት በቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ ሰብእና ውስጥ በእግዚአብሔር ምሕረት፣ በእግዚአብሔር ፍቅር የተዋበና የደመቀ ንጽሕና፣ ብርቱ ትእግስትና የጸና ተስፋ ይታይባት ነበር፡፡ በመጽሐፍ እንደተነገረላት ‹‹ነገርን ሁሉ በልቧ ትጠብቅ›› ለነበረች ለድንግል ማርያም ነፍስን በሚመትር፣ ልብን በሚሰብር ጥልቅ ሐዘኗ ውስጥ በእግዚአብሔር ፍቅር፣ በእግዚአብሔር አሳብና በጎ ፈቃድ የደመቀና የተዋበ ንጽሕናዋ ሐዘኗን አልፎ፣ መከራዋን ድል ነሥቶ የእግዚአብሔር ፍቅር፣ የእግዚአብሔር ውበት በሁለተናዋና በዓይኖቿ ውስጥ ደምቆ ይታይ፣ ጎልቶ ይነበብ ነበር፡፡ ይህችን የፍቅር እናት ይህችን የንጽህናና የፍቅር ተምሳሌት ጌታ በመስቀሉ ላይ ሆኖ እጅግ ይወደው ለነበረው ደቀ መዝሙሩ ለዮሐንስ ‹‹እነኋት እናትህ!›› ሲል የመስቀል ላይ የፍቅር ስጦታውን አበረከተለት፡፡ በእርግጥም ፍቅርን ለሚሰብከው፣ ሁለንተናው በጌታውና በመምህሩ ፍቅር ለነደደና ለተዋበ፣  ለፍቅር ደቀ መዝሙር ለቅዱስ ዮሐንስ የተገባች ስጦታ ነበረች፡፡ ቅድስት ድንግል ማርያም፡፡ በእዚህ ደቀ መዝሙርም በኩል ቅድስት ድንግል ማርያም ለሁላችን እናት ትሆነን ዘንድም በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅነትና ቤዛነት ለሚያምኑ ሁሉ ተሰጠች፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ዘንድ ለቅድስት ድንግል ማርያም ያለው ልዩ ፍቅርና ክብር ውሉ የሚመዘዘው ከዚሁ ከቤተ ልሔም እስከ ጎልጎታ ድንግል ማርያም ከልጇ፣ ከወዳጇ ሳትለይ ባሳየችው ትልቅ ጽናትና የፍቅር ተጋድሎ ነው፡፡ ስለዚህም የቤተ ክርስቲያን ልጆች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን መውደዳችን የመስቀል ላይ ፍቅር ስጦታ በመሆኗ ነው፡፡ እርሷ በእግዚአብሔር የተመረጠች፣ የተከበረች፣ የተወደደች ብጽእት ናትና እንከብራታለን፣ እንወዳታለንም፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን አባት አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው፡- ‹‹. . . ስለዚህ ማርያም ሆይ እንወድሻለን እውነተኛ የጽድቅ መብልንና እውነተኛ የሕይወት መጠጥ የሆነውን ክርስቶስ ኢየሱስን ወልደሽልናልና፡፡›› ብሎ እንዳመሰገነው፡፡

{እኛም የፍቅርን እናት እናመሠግናታለን የፍቅርን እናት ተሰጠን አገኘናትም}

እውነት ለሁሉ

11 Feb, 10:30


ተመልሰናል only Jesus ወንድሞቻችን 😁
በዚች article ላይ መልስ ተብሎ የተሰጠ አለ አይቼዋለውም ከፊሊጶስ ውጭ የፊሊጶስን ባይሉም የሆነ ነገር ለማለት ስላሰብኩኝ ከእሱ ውጭ በአጠቃላይ መልስ ብሎ የመለሰው አካልነት የሚያሳዩ ቁጥሮች ላይ በተዘረዘርው ሲሆን እሱ ላይ እመለስበታለው ከጅምሩም የሥላሴን አካልነት የሚያፈርስም ስላልሆነ የሰጡት መልስ

የተነሳበት ቶፒኩ ኢየሱስ በእኔ ሚኖረው አብ ብሎ በተናገረበት ቃል ላይ ነው ካስታወሱ ኢየሱስ በእኔ ሚኖረው አብ ማለቱ only Jesus አማኞች እንደሚሉት አንድ አካልነትን አደለም  የሚል ነበር የተመለሰው እናም በእኔ ሚኖረው ማለቱ አንድ አካልነት አያሳይም ተብሎ በቀረበበት መልስ ላይ ምንም አይነት ማፍረሻ ምንም ነገር አላመጡም ጥያቄውንም አልመለሱም ጥያቄውን ቢመልሱ በእኔ ሚኖረው ማለቱ አንድ አካልነትን እንደማያሳይ እንጨርስ ነበር ግን ዝምታ መልስ ነውና በዝምታ አልፈዋል እሺ ብለናልም ሁለተኛም እንዳታነሱት እናሳስባለን

እውነት ለሁሉ

10 Feb, 15:49


የክርስቶስ ፍቅር

የክርስቶስ ፍቅር ወደር የሌለውና መለኪያ የሌለው ነው። የሰውን ልጅ ከኃጢአትና ከሞት ለማዳን ሲል ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ሰው የሆነው በታላቅ ፍቅር ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ያለውን ፍቅር በተግባር ያሳየው በመስቀል ላይ ሕይወቱን በመስጠት ነው። እኛን ከዘላለም ሞት ለማዳን ራሱን አሳልፎ ሰጥቷል።

ክርስቶስ በመስቀል ላይ ባፈሰሰው ደም የሰውን ልጅ ከኃጢአት ባርነት ነፃ አውጥቷል። የሞት ፍርሃትን ድል አድርጎ የዘላለም ሕይወት ተስፋን ሰጥቶናል። ስለዚህ፣ ይህን ታላቅ ፍቅር ልንረዳውና በሕይወታችን ልንኖርበት ይገባል።

የክርስቶስ ፍቅር የሕይወታችን መመሪያ ይሁንልን።🙏❤️

እውነት ለሁሉ

10 Feb, 10:39


ገድላት ላይ የተጻፈ ሁሉ መቀበል ግዴታ ከሆነ!!

ጥያቄ:

- “ተአምረ ኢየሱስ” ተብሎ የሚጠራ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ውስጥ አለ(በውጩ አለም ተመሳሳይ ታሪኮችን የያዘው መጽሐፍ የመናፍቃን ነው): እናም በዚህ መጽሐፍ ላይ ጌታችን በሕጻንነቱ ተአምር እንዳደረገ ተዘግቧል..

- ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ደግሞ በዮሐንስ ወንጌል ትርጓሜው ላይ ጌታ በሕጻንነቱ ተአምራትን እየሰራ አልኖረም የመጀመሪያ ተአምር የሰራው ከጥምቀቱ በኋላ ነው ይላል

የቱን ተቀብላችሁ የቱን ትተዉታላችሁ? ያው ተቃራኒ ስለሆነ ማለት ነው እና ደግሞ በምንስ መዝናችሁ? ከኢክቲስ የተወሰደ!!

እውነት ለሁሉ

10 Feb, 07:52


ገድላትን እና ድርሳናትን በአጠቃላይ አዋልድት መጹሀፍትን  አንድ መዕመን በግሉ የመተቸት ተሳስተዋል የማለት የመጣል ስልጣን አለውን ???

በመምህር  ሔኖክ ሀይሌ

እውነት ለሁሉ

09 Feb, 08:48


ኢየሱስ የህያው የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ የሚያምን ሁሉ ስለ እርሱ ሁሌም አበክሮ ሊናገር ይገባዋል ስለ እርሱ መናገር ስለ እርሱ መመስከር፣አንዳንዴ በንጽጽር ተጠምደን ስለ ኢየሱስ እውነት ማውራትን እንዘነጋለን የክርክሮች ርዕሰ ጉዳይ እርሱ ኢየሱስ ቢሆንም በተለየ ሁኔታ ግን እርሱን መተረክ ይገባናልና ስለ ኢየሱስ መናገራችን እንዳይዘነጋ ለማለት ነው🙌

እውነት ለሁሉ

08 Feb, 18:12


ኢየሱስ አብ ነው ?

John 14 አማ - ዮሐንስ
10: እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? እኔ የምነግራችሁን ቃል ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል

only Jesus አማኞች እቺን ጥቅስ በመጠቅስ ለትምህርታቸው ተያይዘዋታል

አንድ አካልነትን ያሳያል ብለው የጠቀሱት ጥቅስ የእራሱ ምዕራፍ እዛው ላይ ሁለት አካልነትን አሳይቶ ነው የጀመረው 
John 14 አማ - ዮሐንስ
1: ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።

በእግዚአብሔር እመኑ በእኔም እመኑ ብሎ ኢየሱስ አብ አለመሆኑን ሁለት ሊታመኑ ሚገቡ ማንነቶች እንዳሉ በመግለጽ ነው የጀመረው ስለዚህ የonly Jesus ትምህርትን ከማይደግፍ እንዲሁም ሊያፈርስባቸው ከሚችል ምዕራፍ መጥቀሱ በጣም ያሳዝናል ሙሉ ምዕራፍን ሳይሆን በአንድ ጥቅስ ላይ ብቻ ስለተመሠረቱ ሌሎችም ጥቅሶች ሁለት አካልነታቸውን ሚገልጽ እንደሆነ እዛው ምዕራፍ ካሉት ውስጥ
{ ቁጥር 13 ኢየሱስ ወደ አብ ሚሄድ ሌላ አካል ነው}
{ቁጥር 15-16 } {ቁጥር 23} 26} ሌሎችም

ዩሀ 14:10 በእኔ የሚኖረው አብ ሚለው ጥቅስ አንድ አካልነት ኢየሱስ አብ መሆኑን ያሳያል ለማለት የማይቀርብ የእራሱ ምዕራፍ እሄን ትምህርት እንደሚቃወመው ከቁጥር 1ጀምሮዋል ሌሎችም ጥቅሶች የተለያዩ አካላት መሆናቸው እንደሚያስረዳ ምዕራፉ አይተናል

ታዳ ኢየሱስ ለምን በእኔ የሚኖረው አብ አለ እዛው ምዕራፍ ለምን እንደሆነ ያለው እዛው ቁጥር ላይ ጨርሶ አጠናቆታል
ኢየሱስ በእኔ ሚኖረው ያለው እንደዚ አይነት ተመሳሳዮችን ሚናገረው አንድ ስልጣን ባህሪ የመለኮት ስራን እንደሚሰሩ ለመናገር የሥላሴን ትምህርት ሚያስረዳ ነው

በእኔ ሚኖረው ያለበት ምክንያት ቁጥር 10ላይ አንድ አካል መሆንን ሳይሆን ስራን እንደሆነ ተገልጿል 👇
John 14 አማ - ዮሐንስ
10: አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል።

በእኔ ሚኖረው አብ ያለበት ምክንያት አንድ አካልነት ነው ሚል ሽታውም የለም በተቃራኒው ስራን ብሎ በእኔ ሚኖረው ያለበት ስራን እንደሆነ እዛው ቁጥር ላይ ጨርሶታል

በሌላም
በውስጥ መኖር ማለት ስራን እንደሆነም እዛው ምዕራፍ ላይ
👇
John 14 አማ - ዮሐንስ
17: እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ።

መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያቶች ውስጥ የሚኖር ተብሎ የተገለጸው ሐዋርያቶች በመንፈስ ተመርተው የእግዚአብሔር ስራ  ስለ መስራት ነው

በዚሁ መሰረት በጥያቄ እናጠቃልለዋለን
በውስጥ መኖር ማለት ስራን መስራት እንደሆነ እዛው ጥቅስ ላይ ዩሀ14:10 እና ቁጥር 17 በመጥቀስ አይተነዋል

ማጠቃለያ ጥያቄአችን በውስጥ መኖር ማለት እንደሚሉን አንድ አካልነት ከሆነ በዚ ቃል መሠረት

John 14 አማ - ዮሐንስ
17: የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ።

በአብ እና በኢየሱስ ንግግር በእኔ አለ በእኔ ሚኖር ማለት እሱ እኔ ነኝ አንድ አካል ማለት ከሆነ መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት የሚኖር ስለተባለ ሐዋርያቶች መንፈስ ቅዱስ ናቸው ያስብላልን ወይ?

የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ከእናንተ ጋር ይሁን።

እውነት ለሁሉ

08 Feb, 07:44


ክርስትናችን የተመሠረተው በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ መሆኑ ግልፅ ነው ኢየሱስ ክርስቶስ አልተነሳም የሚለው ነገር ከተረጋገጠ ክርስትና የሚባል ነገር በእርግጥ አይኖርም፣ እንደዚሁም ደግሞ ኢየሱስ በመስቀል ተሰቅሎ ሞቶ ተቀብሮ በሦስተ ቀን ተነስቷል የሚለው ነገር ከተረጋገጠ እሥልምናና የኢየሱስን ሞቶ መነሳት የሚቃወሙ ቤተ እምነቶች ስህተት መሆናቸውን ይረጋገጣል፣ የዚህ ሁሉ ነገር መሠረት እርሱ ኢየሱስ ነው አያስገርምም In particular, Islam and Christianity are based on their belief in Jesus ያው እሥልምና በኢየሱስ ላይ ባለን አቋም አልተመሠረትንም ቢሉም በኢየሱስ ሞትና ትንሳኤ ባላቸው የተዛባ እምነት ይህ እምነታቸው ስህተት ሆኖ ከተገኘ እስልምናን ትክክል የሚያደርገው ነገር ምን አለ? ምንም።

ወሰላሙ አለይኩም

እውነት ለሁሉ

06 Feb, 14:01


only Jesus isn't biblical study
Matthew 3 አማ - ማቴዎስ
16: ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤
17: እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ “በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፡” አለ።

እውነት ለሁሉ

06 Feb, 07:32


የሕፃናት ቁርባን

ከካቶሊኮች እና የክርስቶስን ሥጋና ደም አማናዊነት ከሚመቀበሉ ፕሮቴስታንቶች ዘንድ አንድ ግርም ያለኝ ልምምድ ሕፃናትን ቁርባን መከልከላቸው ነው። በእነዚህ "አብያተ ክርስቲያናት" ሕፃናትን ማጥመቅ ትክክል እንደኾነ ይታመናል በተለይ በካቶሊክና በሉተራን ዘንድ ሕፃናት የሚጠመቁት ለድኅነትና ለዳግም ልደት ነው። ነገር ግን እንደዚህ ዳግመኛ በክርስቶስ የተወለዱ ሕፃናት ቁርባን ይከለከላሉ። በጥምቀት የክርስቶስ አካላት ከኾኑ የክርስቶስን አካላት ሥጋና ደሙን እንዴት ይከለከላሉ? በተለይ የጥንቷ ቤተክርስቲያን ሕፃናትም መቁረብ እንዳለባቸው በግልጽ ባስተማሩበት ኹኔታ።

ቅዱስ አውግስጢኖስ ዘሂፖ እንዲህ ይላል "በሕፃንነት ውስጥ ኢየሱስ የሚያድነው ምንም ነገር የለውም የሚሉ ለእነዚህ ለሚያምኑ ሕፃናት ክርስቶስ ኢየሱስ መኾኑን እየካዱ ነው ... ኢየሱስ ምን ማለት ነው? ኢየሱስ ማለት መድኃኒት ነው። በእነርሱ ምንም የሚያድነው የለም ማለት ክርስቶስ ለእነርሱ ኢየሱስ አይደለም ማለት ነው። ለተጠመቁ ሰዎች ክርስቶስ ኢየሱስ አይኾንላቸውም የሚለውን ሃሳብ የምትታገሱ ከኾነ እምነታችሁ ጤናማና ርቱዕ ነው የሚለው ያጠራጥረኛል። አዎ ሕፃናት ናቸው ነገር ግን ምሥጢራቱን ይቀበላሉ፤ ሕፃናት ናቸው ነገር ግን በራሳቸው ሕይወት እንዲኖራቸው ከጠረጴዛው ይካፈላሉ።" (Augustine, Sermon 174, 7)

የሐዋርያት ድንጋጌም እንዲህ ይላል "ጸሎቱን የጸለያችሁ ንዑሰ ክርስቲያን ፣ ሰሚዎችና መናፍቃን ኹሉ ውጡ ማንም አይቆይ። እናቶችም ከልጆቻቸው ጋር ይቁረቡ" (Constitutions of the Holy Apostles, 8.2.12)

ኢየሱስ የሕፃናትም መድኃኒት ነው!

ኪዳን ዘኢየሱስ

እውነት ለሁሉ

05 Feb, 15:08


አማኑኤል ይቅር ባይ ነው ፍቅር
ምሕረት ከብቦት በሰማያት የሚኖር
......................................
“አማኑኤል ሆይ፥ የክንፉ መዘርጋት የአገርኽን ስፋት ትሞላለች።”ኢሳይያስ 8፥8

“ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።”ኢሳ 7፥14

“እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።” ማቴ 1፥23

የጌታ አማኑኤል ምሕረት ቸርነትና ይቅርታው ይብዛልን አሜን !!
🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰🥰
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!!

እውነት ለሁሉ

05 Feb, 07:17


Church Infallibilityን ያልተረዳ ሙግት

"ቤተክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስ ጠባቂና ባለ አደራ ናት ነገር ግን ይህ ብቻ ቤተክርስቲያንን infallible አያደርጋትም በአንድ ነገር ትክክል ኾነች ማለት በኹሉ ነገር ትክክል ናት ማለት አይደለምና።" የሚለው የፕሮቴስታንቶች ሙግት ነው። ነገር ግን ይህ ሙግት የቤተክርስቲያንን አይሳሳቴነት የተረዳ አይመስልም እኛ ቤተክርስቲያን በኹሉ ነገር ትክክል ናት አላልንም እኛ ያልነው ቤተክርስቲያን በአባቶች ስምምነት ባስተማረችው አስተምህሮ ላይ ስህተትን ልትሠራ አትችልም ነው።

ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን ስትወስን ከተጠቀመቻቸው መሥፈርቶች ውስጥ "ሐዋርያዊ ጸሐፊነት (ከሐዋርያትና የእነርሱ ቅርብ ደቀ መዛሙርት) ፣ ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነትና ትክክለኛ አስተምህሮ" ይገኙበታል። መሥፈርቶቹ እነዚህ መኾናቸውን ፕሮቴታንቶች ራሱ የሚቀበሉት ነው። እስቲ ከነዚህ መሥፈርቶች ትክክለኛ አስተምህሮን ለይተን እንየው። ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን ስትወስን ከነበሩት መጽሐፍት ውስጥ ትክክለኞቹን የለየችው ከሐዋርያት በተቀበለችው ትክክለኛ አስተምህሮ መዝና ነው የቤተክርስቲያን አስተምህሮ ደግሞ ሊሳሳት ስለማይችል መጽሐፉም ሊሳሳት አይችልም እንላለን።

ፕሮቴስታንቶች ግን ቤተክርስቲያን በአስተምህሮዋ ልትሳሳት ትችላለች ብቻ ሳይኾን ተሳስታለች ብለው ያምናሉ ስለዚህ ቤተክርስቲያን የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍትን የመረጠችው በተሳሳተ መሥፈርት ነው። መሥፈርቱ ከተሳሳተ ደግሞ የመሥፈርቱ ውጤትም ስህተት ያለበት ነው የሚኾነው። Fallible list of infallible books ነው የምንቀበለው ቢሉ ራሱ እነዛ listኡ ብቻ ሳይኾን መጽሐፍቱም ጭምር ከመጀመሪያውኑ infallible ለመኾናቸው ምሥክርነት አይኖራቸውም መጽሐፍቱ ራሱ የተመረጡት በተሳሳተ መሥፈርት ላይ ተመርኩዘው ነውና።

{ኪዳን ዘኢየሱስ} እንጻፈው!!

እውነት ለሁሉ

04 Feb, 08:48


{አህመዲን ጀበል} ጠየቂ👀
መጽሐፍ ቅዱስ በሉቃስ ወንጌል 22: 3 -5 “ሰይጣንም ከአሥራ ሁለቱ ከተቆጠረው አንዱ በነበረው የአስቆሮቱ በተባለው በይሁዳ ገባበት፤  ሄዶም እንዴት አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከካህናት አለቆችና ከመቅደስ አዛዦች ጋር ተነጋገረ፡፡ እነርሱም ደስ አላቸው፥ ገንዘብም ሊሰጡት ተዋዋሉ፡፡ እርሱም በነገሩ ተስማማ” ይላል፡፡ ሰይጣን በይሁዳ ገብቶ ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጥ ካደረገውና ክርስቲያኖች እንደሚሉት ኢየሱስም ተይዞ ከተሰቀለ ሰይጣን ለክርስቲያኖች ባለ ውለታ ሆኗል ማለት ነው፡፡?ለምን ቢሉ ክርስቲያኖች እንደሚሉት በኢየሱስ መሰቀል ነውና “ድነው ከኃጢአት ነጻ የወጡት፤ ገነትም ወራሽ የሆኑት፡፡”  ይህ ነው የክርስትና መዳኛ መንገድ፡፡ ስለዚህ ሰይጣን በይሁዳ ገብቶ ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጥ አደረገው፡፡ ከዚያም ክርስትና እንደሚለው ኢየሱስ ተይዞ ተሰቀለ፡፡ በጥሞና ካስተዋልነው ክርስቲያኖች “ድነናል” ያሉበት “ስቅለት” እንዲሳካ ሰይጣን ግንባር ቀደም አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ የመዳኛውን መንገድ ዘርግቷል፡፡ ታድያ የክርስትና አብዩ አስተምህሮትና መዳኛው የሰይጣን ሊሆን አይደል? ሰይጣን በይሁዳ ገብቶ ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጥ ባያደርግ ኖሮ ስቅለት ይሳካ ነበር? ክርስትና እንደሚለው ክርስቶስ ባይሰቀል ክርስትያኖች ከኃጢአት ይነጹ ነበርን? ክርስትና የሚባል እምነትስ ይኖር ነበርን? በፍፁም!! ታድያ እንደ ሰይጣን ማን መልካም ሰሪ አለ? ኢየሱስን አሰቅሎ ክርስትያኖችን አድኖ የለም እንዴ?

አሕመዲን ጀበል ይህንን ጥያቄ ያቀረቡበት መንገድ ከምሑራዊ አካሄድ ያፈነገጠ፣ ድፍረትና ንቀት የታከለበት እንዲሁም የክርስትናን ትምህርት በሚያንቋሽሽ አነጋገር ነው፡፡ አካሄዳቸውን በማበላሸት ገና ከጅምሩ ኩሬውን መርዘውታል፤ የማስተማር ፍላጎታቸውንና ቅንነታቸውንም እንድንጠራጠር አድርገውናል፡፡ የክርስቶስ ወደ ምድር መምጣትና ስለ ሰው ልጆች ኃጢኣት መሞት የእግዚአብሔር ዘለዓለማዊ እቅድ እንጂ የየትኛውም ፍጥረት ዕቅድ አልነበረም (ራዕይ 13፡8፣ የሐዋርያት ሥራ 4፡27-28)፡፡ ወደ ምድር የመጣውም በገዛ ፈቃዱ ነፍሱን ስለ ብዙዎች ቤዛ ለማድረግ እንጂ ተገዶ አይደለም (ዮሐንስ 10፡11፣ 10፡15፣ 10፡17-18 15፡13፣ ማርቆስ 10፡45)፡፡ ስለ ሞቱና ስለ ትንሣኤው አስቀድሞ መናገሩን በብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ እናነባለን (ማቴዎስ 12፡38-40፣ 16፡21፣ 17፡22-23፣ 20፡18-10፣ 21፡33-46፣ 26፡21-32፣ 26፡36-40፣ 26፡61-62፣ ማርቆስ 8፡31፣ 9፡9፣ 9፡30-31፣ 10፡33-34፣ 10፡45፣ 12፡1-12 14፡18-28፣ 14፡32-40፣ ሉቃስ 9፡22፣ 11፡29-30፣ 13፡32-33፣ 20፡9-19፣ 22፡15-20፣ 22፡39-46፣ ዮሐንስ 3፡13-14፣ 8፡28፣ 12፡32-34)፡፡ ስለዚህ የክርስቶስ ሞት በሰይጣን የታቀደ አልነበረም፡፡ ሰይጣንም ሆነ በአፅናፈ ዓለም ውስጥ የሚገኝ የትኛውም ፍጥረት በእግዚአብሔር እንደተፈጠረ፣ በእርሱ ሉኣላዊ ሥልጣን ስር እንደሚገኝና እግዚአብሔር አምላካችን የሁሉ የበላይ እንደሆነ ክርስትና ያስተምራል (ዳንኤል 4፡35፣ 2ዜና 29፡14፣ 20፡6፣ ዘዳግም 10፡14፣ ነህምያ 9፡6፣ ራዕይ 4፡11)፡፡ ሰይጣን ከእግዚአብሔር ቁጥጥር ውጪ እንደሆነ ማሰብና የእግዚአብሔር ተፎካካሪ አካል አድርጎ መሳል የእግዚአብሔርን ሉኣላዊ ሥልጣን ያለማወቅ ነው፡፡ ሰይጣን የይሁዳን ክፉ ምኞት በመጠቀም ኢየሱስን አሳልፎ እንዲሰጥ ሲያደርገው የእግዚአብሔርን ዘለዓለማዊ ዕቅድ በመረዳትና የራሱን የሽንፈት መንገድ እያመቻቸ መሆኑን በማወቅ አልነበረም፡፡ ይህንን በማድረጉ እንደ ይሁዳ ሁሉ ሰይጣንም ራስን የማጥፋት ተግባር ፈፅሟል፡፡ የኢየሱስ ሞት ሰይጣንን አዋርዶታ፡፡ ትንሣኤው ደግሞ እስከ ወዲያኛው ኃይሉን አንኮታኩቶታል! ሰይጣን በየዘመናቱ የእግዚአብሔር ዕቅድ ውስጥ ጣልቃ በመግባት ለማበላሸት ቢሞክርም እግዚአብሔር ግን የዕውቀቱን ምጡቅነት እና የጥበቡን ልቀት በማሳየት ሰይጣንን ሲያዋርደው እንመለከታለን፡፡ ለምሳሌ ያህል ሰይጣን ኢዮብን ሲፈትነው ፃድቅ የሆነውን ኢዮብን ከእግዚአብሔር በመለየት ለማጥፋ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ግን የሰይጣንን ፈተና የኢዮብን እምነትና ፅድቅ ለመግለጥ እና ለትውልዶች ሁሉ ማስተማርያ ለማድረግ ተጠቅሞበታል፡፡ ሰይጣንም ዕቅዱ ግቡን ሳይመታ ቀርቶ አፍሯል፡፡ የኢየሱስም ስቅለት እንደዚያው ነው፡፡ የተዋረደው ሰይጣን ዛሬ በእነ አሕመዲን በኩል በመምጣት ውርደቱንና ሽንፈቱን ለማስተባበል ቢሞክር አንሰማውም፣ አንቀበለውም፡፡

    ምንጭ {ewnet lehulu} ድኀረ ገፅ!!

እውነት ለሁሉ

04 Feb, 06:01


🚩 የዕብራውያን ጸሐፊ

https://t.me/TheTriune/1184 (ክፍል 1)

https://t.me/TheTriune/1186 (ክፍል 2)

https://t.me/TheTriune/1192 (ክፍል 3)

https://t.me/TheTriune/1215 (ክፍል 4)

እውነት ለሁሉ

03 Feb, 20:06


አስተማሪ ትምህርት አይሻ አስተላልፋለች የመዳን ቀን ዛሬ ነው እያለን
ከእራሳቸው አስተምህሮ መጻህፍት ቁርአን ለምን እንደመጣ ያስተምራል በማለት የያዝነውን በዜና መልክ ይቀርባል

ሰበር ዜና  ማንኛውም ሴት ለነብዩ እንደፈለጉ አማኞችን እንዲያገቡ ደስ ያላቸውን ያሻቸውን በሙሉ የበላይ ሀላፊ የሆነው አላህ ፈቅዷልም መሀመድ የሰላሳ ሰው ጉልበት የሰጠው አላህ ሚስቶቹን እንደፈለገ ያለለከት እንዲያገባ አላህ ለዚህ የሚሆን ለእሱ ፍላጎቱን ሚያሟላ አያም አውርዷል 🥸

አይሻም ለራሱ እንዲ ስትል መስክራለችም "አላህ ያንተን ፍላጎት" "ለማሟላት ይፈጥናል" በማለት ቁርአን የመሀመድን ፍላጎት ለማሟላት የመጣ መጽሀፍ እንደሆነ አይሻ አስተላልፋለች

A'isha (Allah be pleased with her) reported:
I felt jealous of the women who offered themselves to Allah's Messenger (ﷺ) and said: Then when Allah, the Exalted and Glorious, revealed this:" You may defer any one of them you wish, and take to yourself any you wish; and if you desire any you have set aside (no sin is chargeable to you)" (xxxiii. 51), I ('A'isha.) said: It seems to me that your Lord hastens to satisfy your desire.

አይሻ(ረ.ዓ) እንዳስተላለፈችው :-ለአላህ መልእክተኛ(ﷺ) እራሳቸውን እየመጡ አሳልፈው በሚሰጡ ሴቶች ቅናት ተሰማኝ: አላህ ሱብሃነሁ ወተኣላ ይህንን አያ አወረደ (ቁርአን 33:51):- ከእነርሱ(ከሴቶቹ)  መሀል የምትፈልጋትን ታቆያለህ፡፡ የመረጥሃትንም ሴት ለራስህ ትወስዳለህ ፡፡ የትውካትንም ሴት መልሰህ ብትፈልጋት ወደራስህ ብታስጠጋት በአንተ ላይ ኀጢአት የለብህም፡፡
አይሻ(ረ.ዓ) እንዲህ አለች " እኔ እንደሚመስለኝ ጌታህ(አሏህ) ያንተን ፍላጎት ለሟሟላት ይፈጥናል::"

حَدَّثَنَا أَبُو كُرَيْبٍ، مُحَمَّدُ بْنُ الْعَلاَءِ حَدَّثَنَا أَبُو أُسَامَةَ، عَنْ هِشَامٍ، عَنْ أَبِيهِ، عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ كُنْتُ أَغَارُ عَلَى اللاَّتِي وَهَبْنَ أَنْفُسَهُنَّ لِرَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم وَأَقُولُ وَتَهَبُ الْمَرْأَةُ نَفْسَهَا فَلَمَّا أَنْزَلَ اللَّهُ عَزَّ وَجَلَّ ‏{‏ تُرْجِي مَنْ تَشَاءُ مِنْهُنَّ وَتُؤْوِي إِلَيْكَ مَنْ تَشَاءُ وَمَنِ ابْتَغَيْتَ مِمَّنْ عَزَلْتَ‏}‏ قَالَتْ قُلْتُ وَاللَّهِ مَا أَرَى رَبَّكَ إِلاَّ يُسَارِعُ لَكَ فِي هَوَاكَ.

Reference : Sahih Muslim 1464 a
In-book reference : Book 17, Hadith 64
USC-MSA web (English) reference : Book 8, Hadith 3453(deprecated numbering scheme)

ማንኛዋም ሴት ነብዩ መሀመድ ከፈለገ ነብዩ አግብቶ ወሲብ እንዲያደርግ አላህ ፈቅዶለታል
አላህ የፈቀደለት አያ ከፍ ሰንል እዛው ላይ ያመነች ሴት ራሷን ለነብዩ ስጦታ እንድታረግ የመሰሳሉት የመሀመድ ፍላጎቶች የመሳሰሉት እንደሚከተለው ይቀርባል የሙሀመድን ፍላጎት አላህ ባወረደለት አያ ውስጥ ከፍ ስንል ባኘነው አያ ላይ

የአሕዛብ ምዕራፍ 33÷50

يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ إِنَّا أَحْلَلْنَا لَكَ أَزْوَاجَكَ اللَّاتِي آتَيْتَ أُجُورَهُنَّ وَمَا مَلَكَتْ يَمِينُكَ مِمَّا أَفَاءَ اللَّهُ عَلَيْكَ وَبَنَاتِ عَمِّكَ وَبَنَاتِ عَمَّاتِكَ وَبَنَاتِ خَالِكَ وَبَنَاتِ خَالَاتِكَ اللَّاتِي هَاجَرْنَ مَعَكَ وَامْرَأَةً مُّؤْمِنَةً إِن وَهَبَتْ نَفْسَهَا لِلنَّبِيِّ إِنْ أَرَادَ النَّبِيُّ أَن يَسْتَنكِحَهَا خَالِصَةً لَّكَ مِن دُونِ الْمُؤْمِنِينَ ۗ قَدْ عَلِمْنَا مَا فَرَضْنَا عَلَيْهِمْ فِي أَزْوَاجِهِمْ وَمَا مَلَكَتْ أَيْمَانُهُمْ لِكَيْلَا يَكُونَ عَلَيْكَ حَرَجٌ ۗ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا

አንተ ነቢዩ ሆይ! እኛ እነዚያን መህሮቻቸውን የሰጠሃቸውን ሚስቶችህን፣ አላህ ባንተ ላይ ከመለሰልህም እነዚያን እጅህ የጨበጠቻቸውን ምርኮኞች፣ እነዚያንም ከአንተ ጋር የተሰደዱትን የአጎትህን ሴቶች ልጆች፣ የአክስቶችህንም ሴቶች ልጆች፣ የየሹማህንም ሴቶች ልጆች፣ የየሹሜዎችህንም ሴቶች ልጆች (ማግባትን) ለአንተ ፈቅደንልሃል፡፡
  👉የአመነችንም ሴት ነፍሷን (ራሷን) ለነቢዩ ብትሰጥ
ነቢዩ ሊያገባት የፈለገ እንደ ኾነ ከምእምናን ሌላ ላንተ ብቻ የጠራች ስትኾን (ፈቀድንልህ)፡፡
  በእነርሱ (በምእምናን) ላይ በሚስቶቻቸውና እጆቻቸው በጨበጧቸው (ባሮች ነገር) ግዴታ ያደረግንባቸውን በእርግጥ ዐውቀናል፡፡ ባንተ ላይ ችግር እንዳይኖር (ያለፉትን ፈቀድንልህ)፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡

አላህም ለመሀመድ ያወረደለት አያ በሀዲሱ ላይ ያለ ቢሆንም በተጨማሪ እዚህላይ እኔም እንደ አይሻ አላህ የሙሀመድን ፍላጎት ለማሟላት እንደሚፈጥንና በቁርአኑም  ስለተገረምኩበት ድጋሜ ለጥፈዋለው


۞ تُرْجِي مَن تَشَاءُ مِنْهُنَّ وَتُؤْوِي إِلَيْكَ مَن تَشَاءُ ۖ وَمَنِ ابْتَغَيْتَ مِمَّنْ عَزَلْتَ فَلَا جُنَاحَ عَلَيْكَ ۚ ذَٰلِكَ أَدْنَىٰ أَن تَقَرَّ أَعْيُنُهُنَّ وَلَا يَحْزَنَّ وَيَرْضَيْنَ بِمَا آتَيْتَهُنَّ كُلُّهُنَّ ۚ وَاللَّهُ يَعْلَمُ مَا فِي قُلُوبِكُمْ ۚ وَكَانَ اللَّهُ عَلِيمًا حَلِيمًا

ከእነርሱ የምትሻትን ታቆያለህ፡፡ የምትሻውንም ወደ አንተ ታስጠጋለህ፡፡ (በመፍታት) ከአራቅሃትም የፈለግሃትን (በመመለስ ብታስጠጋ) በአንተ ላይ ኀጢአት የለብህም፡፡ ይህ ዓይኖቻቸው ወደ መርጋት፣ ወደ አለማዘናቸውም፣ ለሁሉም በሰጠሃቸው ነገር ወደ መውደዳቸውም በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህም በልቦቻችሁ ውስጥ ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡ አላህም ዐዋቂ ታጋሽ ነው፡፡
የአህዛብ ምዕራፋ
33÷51 ላይ ይገኛል

@kettegawa_ewnet

እውነት ለሁሉ

03 Feb, 06:53


የሕፃናት ቁርባን

ከካቶሊኮች እና የክርስቶስን ሥጋና ደም አማናዊነት ከሚመቀበሉ ፕሮቴስታንቶች ዘንድ አንድ ግርም ያለኝ ልምምድ ሕፃናትን ቁርባን መከልከላቸው ነው። በእነዚህ "አብያተ ክርስቲያናት" ሕፃናትን ማጥመቅ ትክክል እንደኾነ ይታመናል በተለይ በካቶሊክና በሉተራን ዘንድ ሕፃናት የሚጠመቁት ለድኅነትና ለዳግም ልደት ነው። ነገር ግን እንደዚህ ዳግመኛ በክርስቶስ የተወለዱ ሕፃናት ቁርባን ይከለከላሉ። በጥምቀት የክርስቶስ አካላት ከኾኑ የክርስቶስን አካላት ሥጋና ደሙን እንዴት ይከለከላሉ? በተለይ የጥንቷ ቤተክርስቲያን ሕፃናትም መቁረብ እንዳለባቸው በግልጽ ባስተማሩበት ኹኔታ።

ቅዱስ አውግስጢኖስ ዘሂፖ እንዲህ ይላል "በሕፃንነት ውስጥ ኢየሱስ የሚያድነው ምንም ነገር የለውም የሚሉ ለእነዚህ ለሚያምኑ ሕፃናት ክርስቶስ ኢየሱስ መኾኑን እየካዱ ነው ... ኢየሱስ ምን ማለት ነው? ኢየሱስ ማለት መድኃኒት ነው። በእነርሱ ምንም የሚያድነው የለም ማለት ክርስቶስ ለእነርሱ ኢየሱስ አይደለም ማለት ነው። ለተጠመቁ ሰዎች ክርስቶስ ኢየሱስ አይኾንላቸውም የሚለውን ሃሳብ የምትታገሱ ከኾነ እምነታችሁ ጤናማና ርቱዕ ነው የሚለው ያጠራጥረኛል። አዎ ሕፃናት ናቸው ነገር ግን ምሥጢራቱን ይቀበላሉ፤ ሕፃናት ናቸው ነገር ግን በራሳቸው ሕይወት እንዲኖራቸው ከጠረጴዛው ይካፈላሉ።" (Augustine, Sermon 174, 7)

የሐዋርያት ድንጋጌም እንዲህ ይላል "ጸሎቱን የጸለያችሁ ንዑሰ ክርስቲያን ፣ ሰሚዎችና መናፍቃን ኹሉ ውጡ ማንም አይቆይ። እናቶችም ከልጆቻቸው ጋር ይቁረቡ" (Constitutions of the Holy Apostles, 8.2.12)

ኢየሱስ የሕፃናትም መድኃኒት ነው!

{ኪዳን ዘኢየሱስ}

እውነት ለሁሉ

03 Feb, 05:24


“አብ በራሱ ሕይወት እንደለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታል” የሚለው ከኢየሱስ አምላክነት አኳያ እንዴት ይታያል?
የአምላክ ሕልውና በማንም ላይ ጥገኛ አይደለም፤ አይኾንምም፡፡ በዮሐንስ ወንጌል 5፡26 ላይ መጽሐፍ ቅዱስ “አብ በራሱ ሕይወት እንደለው እንዲሁ ደግሞ ለወልድ በራሱ ሕይወት እንዲኖረው ሰጥቶታል” ይላል፡፡ ነገር ግን እንደዚህኛው ጥቅስ ገለጻ የኢየሱስ ሕልውና በአብ (አምላክ) ላይ ጥገኛ ነው፡፡ “ለወልድ በራሱ ሕይወት አንዲኖረው ሰጥቶታል” ይላል፡፡ ወልድ ሕልውና (ሕይወት) ያገኘው አብ ስለሰጠው ነው፡፡ የኢየሱስ ሕልውና በአብ ላይ ጥገኛ ነው፡፡ ኢየሱስ ያለ አብ በራሱ ሕልውና ሊኖረው ካልቻለ እንዴት አምላክ ሊሰኝ ይችላል?

ይህ የኢየሱስን ዘለዓለማዊ መገኘት (Eternal Generation) የሚያመለክት በመኾኑ የሥላሴን አስተምሕሮ የሚደግፍ ነው፡፡ በሥላሴ አስተምሕሮ መሠረት ኢየሱስ በዘለዓለማዊ መገኘት ከአብ የተገኘ ነው፡፡ ለዚህ ነው የኒቅያ የሃይማኖት መግለጫ “ከአምላክ በተገኘው አምላክ፣ ከብርሃን በተገኘ ብርሃን፣ ከእውነትኛ አምላክ በተገኘ እውነተኛ አምላክ፣ በተፈጠረ ሳይኾን በተወለደ…” የሚሉ አንቀፆችን ያካተተው፡፡ የኢየሱስ ሕይወት ከአብ የተገኘ ነው፡፡ ይህ መገኘት ዘለዓለማዊና በጊዜ ያልተገደበ ሲሆን የኢየሱስን መለኮታዊ ባሕርይ ከአብ አያሳንስም፡፡ አብ ያሉት ባሕርየ መለኮታት ኹሉ ወልድም አሉት፡፡በሌላ አባባል ለመኖር በማንም ላይ ጥገኛ ያልሆነው የአብ ሕይወት የወልድም ሕይወት ነው ማለት ነው፡-
“እግዚአብሔርም የዘለዓለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው፡፡ ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም፡፡” (1ዮሐንስ 5፡11-12)፡፡
እግዚአብሔርን በትክክል መግለፅ የሚችል ምሳሌ ባይኖርም የወልድን ዘለዓለማዊ መገኘት ለመረዳት ተከታዩ ምሳሌ ይረዳል፡፡ እስኪ በጊዜ ያልተገደበ ከዘለዓለም ዘመናት በፊት ሲያበራ የነበረ አንድ ኮከብ አስቡ፡፡ ብርሃኑ ኮከቡ በነበረበት ጊዜ ኹሉ አብሮት ነበር፡፡ ነገር ግን የኮከቡ ብርሃን ከኮከቡ የተገኘ ነው፡፡ ብርሃኑ ከሌለ ኮከብነቱ ይቀራል፡፡ ኮከቡ ከሌለ ብርሃኑም ሊኖር አይችልም፡፡ የአብና የኢየሱስንም ቁርኝት በዚህ መንገድ መረዳት ይቻላል፡፡ ለዚህ ነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርሱና አብ አንድ መሆናቸውን፤ እርሱን ያየ አብን ማየቱን እዲሁም እርሱ በአብ አብም ደግሞ በእርሱ እንዳለ የተናገረው (ዮሐ. 14፡9-11)፡፡ “አብ” እና “ወልድ” የሚሉት መጠርያዎች ይህንን ዘለዓለማዊ አንድነት የሚገልፁ ናቸው፡፡

ምንጭ {ewnetlehulu) ድኀረ ገፅ!!

እውነት ለሁሉ

02 Feb, 07:50


{ገድላትን ሳልቀበል ክርስቲያን መሆን እችላለሁ}?

አሁን ላይ የብዙዎቹ ጭንቀት የሆነ ነገር ቢኖር ይህ ጥያቄ ይመስለኛል personali እንዳስተዋልኩት ማለቴ ነው፣ እናም እናንተ ጌታ ኢየሱስ የሚወዳችሁ ሰዎች ጌታችን ኢየሱስ እጅጉኑ አብዝቶ ይወዳቹኃል፣ ስለ እናንተ ብሎ የባርያን መልክ በመያዝ እስከ ሞት ድረስ ዋጋ የከፈለላችሁ ናችሁ እናም ክርስቲያን ለመሆን ገድል፣ተዓምር፣ድርሳን፣ እነዚህ ነገሮች ክርስቲያን የመሆን መስፈርት አይደሉም። ስለዚህም ልትጨነቁበትና ጥያቄ ሊፈጥርባችሁ አይገባም፣ ክርስቲያን ለመሆን {እርሱ ኢየሱስ የህያው የእግዚአብሔር ልጅ ነው} ብሎ ማመን እና በኢየሱስ በኩል የመጣው እውነተኛው የክርስቶስን ትምህርት አምኖ ተቀብሎ መጠመቅ ነው የሚጠበቅባችሁ፣ይህንን ካደረጋችሁ የክርስቶስ ሙሽራ ወደሆነቺው ወደ ቤተክርስቲያን ትጨመራላችሁ የክርስቶስ አካል ትሆናላችሁ ማለት ነው።

ከዚህ ባለፈ ግን እንደው ክርስትናን ከተቀበልኩ በኋላ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ መጻሕፍትን እንዴት ልቀበል፣ የሚከብዱና ከትምህርቴ ጋር የሚጋጩ ነገር ካገኘሁ የሚል ነገር ከመጣ በጣም ቀላል ነገር Get over these things and let them go ነው። ገና ከጅምሩ ከቤተክርስቲያን {አስተምህሮ} ጋር የሚጣረስ ነገር ቢኖር እራሱ ቤተክርስቲያን ስለማትቀበለው ማለት ነው። እናም እናንተ ጌታ የሚወዳችሁ ሰዎች ኑ ወደ ኢየሱስ እርሱ ኢየሱስ ይወዳቹኃልና።

     {መልካም ዕለተ ሰንበት}

እውነት ለሁሉ

02 Feb, 07:47


የጥቁር አሜርካውያን የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያን የኢትዮፕያ ኦርቶዶክስ መጹሀፍ ቅዱስ 80 አሀዱን በይፋ ተቀበሉት ❤️🙏

እውነት ለሁሉ

31 Jan, 13:26


🚩 የመሲሁ ዳግም ምጽአት በብሉይ ኪዳን

https://t.me/TheTriune/1001 (ክፍል 1)

https://t.me/TheTriune/1003 (ክፍል 2)

https://t.me/TheTriune/1008 (ክፍል 3)

https://t.me/TheTriune/1010 (ክፍል 4)

https://t.me/TheTriune/1012 (ክፍል 5)

https://t.me/TheTriune/1020 (ክፍል 6)

https://t.me/TheTriune/1023 (ክፍል 7)

እየገባችሁ እኒህን የመሰሉ አርቲክሎች በላ በላ አድርጉ lol samiንም አበረታቱት

እውነት ለሁሉ

30 Jan, 17:11


ዩሐንስ ወንጌል ምዕራፍ 10:38
ይህ ጥቅስ ኢየሱስ አብ መሆኑን ያሳያል?

ዩሀ 10:30ን አብና ኢየሱስ የተለያዩ አካላት መሆናቸውን ያሳያልን ስንል ቁጥር 38 በመጥቀስ ለሰው ሰራሽ ኢ መጽሀፍ ቅዱሳዊ ሀሳብ ይጠቅሱታል

የonly Jesus እምነት በመጽሀፍ ቅዱስ ሽታውም አይገኝም ቁጥር 38 የሥላሴን አስተምህሮ መገናዘብን የሶስቱ አካል አንድነት ስልጣንን የሚያሳይበት ነው በፍጹም ኢየሱስ አብ መሆኑን ሚያሳይ አደለም

እስኪ ጥቅሱን እንመልከት
John 10 አማ - ዮሐንስ
38: ባደርገው ግን፥ እኔን ስንኳ ባታምኑ አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።”


እንደዚ ማለቱ ኢየሱስ አብ መሆኑን ሳይሆን አንድ ስልጣን መኖራቸውን እንድትን ሚያሳይ ነው ለምን ብንል ቁጥር 25 እንደዚ ይላል

John 10 አማ - ዮሐንስ
25: ኢየሱስም መለሰላቸው፥ እንዲህ ሲል፦ “ነገርኋችሁ፡ አታምኑምም፡ እኔ በአባቴ ስም የማደርገው ሥራ ይህ ስለ እኔ ይመሰክራል፤

ኢየሱስ በአብ ስም( ስልጣን) መምጣቱን ሁለቱ የተለያዩ አካላት አብና ኢየሱስ አንድ ስልጣን መለኮት መኖራቸውን 
በ contextual ደረጃ ቁጥር 38 ያስረዳናል እንጂ አንድ አካል መሆንን አደለም እሄ ብቻ ሳይሆን እንደዚ አይነት ተመሳሳይ ጥቅሶች በዚሁ መሠረት ሚቃኙ ናቸው

ኢየሱስ ከመጀመሪያው ጀምሮ በአብ ስም መምጣን አስረድቶ ቁጥር 30 እኔና አብ አንድ ነን ብሎ አንድ ስም (ስልጣንን) እና እኔና አብ በማለት ሁለት የተለያዩ አካል መሆናቸውን ኢየሱስና አብ ተናግሮ
ቁጥር 38 አብ በእኔ እኔም በአብ እንዳለሁ ሚለው በአዉዱ መሠረት ቁጥር 25 ላይ እንደተገለጸው ስለ ስም ስለ ስልጣን እያስረዳ ነው  ስም ስልጣንን የሚያመላክት ቃል ስለሆነ በሐዋርያት ስራ ምዕ 4:7 ላይ ስም ስልጣንን ሚያመላክት መሆኑን እንደተገለጸውም

ዩሀንስ ወንጌል ምዕ10:25 ስለ ስም ስለ (ስልጣንን) እየተናገረ ስለሆነ
ቁጥር 38
John 10 አማ - ዮሐንስ
38:አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።”    አለ።።።


የኢየሱስና አብ አንድ ስልጣን ሀይል መኖራቸውን መገናዘባቸው ሥላሴ አማኞች ምስጢረ ሥላሴን ከምናስረዳበት ጥቅሶች ውስጥ አንዱ ነው እሄ ብቻ ሳይሆን እንጀዚ አይነት ተመሳሳይ ጥቅሶችም በእንደዚ በሥሌሴአዊ አስተምህሮ ሚቃኙ ናቸው

ታዳ በመጽሀፍ ቅዱስ መሠረት በተመለሰላቸው ላይ ማፍረሻ ስለሌላቸው መጀመሪያ ላይ የተማመነውን መልሰው ይጠይቃሉ ምን... አንድ ከሆነ ስልጣናቸው ለምን በኔ ስም አላለም ? ይህ ጥያቄ ግን የተመለሰ ነበር

John 10 አማ - ዮሐንስ
30: እኔና አብ አንድ ነን።” እኔና አብ በማለት ሁለት መሆናቸውን ኢየሱስና አብ በማለት ተናግሮ

ከአብጋ በሁሉም በስልጣንም አንድ መሆኑን ደሞ አንድ ነን በማለት የተናገረበትን የአብ ስም (ስልጣን) የኢየሱስም መሆኑን እዚጋ ጨርሰን ነበር  የተመለሰ ጥያቄ ላለመቀበል ተብሎ የሚደረግ ጥረት ነው እንጂ እየተመለሰ ነበር

በዚህ መሠረት ዩሀንስ ወንጌል 10:38 አንድ አካል መሆናቸውን ነው ሚያሳየው ትክክል አደለህም ሚል ማፍረሻ ያለው ሰው ማቅረብ ይችላል ከልጅ ሚኪ ትክክለኛው አምላክ አምናችሁ ዳኑ

በተነሳበት ርእስ ላይ በጥያቄ ይቆጫል  ...
John 10 አማ - ዮሐንስ
38: አብ በእኔ እንደ ሆነ እኔም በአብ እንደ ሆንሁ ታውቁና ታስተውሉ ዘንድ ሥራውን እመኑ።”

እንደዚ ማለቱ
አንድ አካል ቢሆኑ እንዴት አብ በእኔ አለ ወይም እኔ በአብ አለው ይባላል እኔ አብ ነኝ ወይም አብ እኔ ነኝ ይላል እንጂ። አብ ብሎ የሆነን አካል ጠርቶ በእኔ ካለ በግልጥ ሁለት አካልነታቸውን የሚያመለክት ነው

ለምሳሌ አንድ ጥቅስ እንይ
ዮሴፍ
Genesis 37 አማ - ዘፍጥረት
8: ወንድሞቹም፦ “በእኛ ላይ ልትነግሥብን ይሆን?

እዚጋም ተመሳሳይ ነው ከኢየሱስጋ ሁለት ብቻ ስለሆነ ነው የዮሴፍ ከዛ በላይ ኢየሱስ አብ በእኔ እንዳለ እኔም በአብ እንዳለሁ ያለው በናተ መሠረት ግን ogዎች

የዮሴፍ ወንድሞቹ ሌላ አካል ናቸው።
ዮሴፍም ሌላ አካል ነው
በእኛ ላይ ልትነግስብን ይሆን ብለው የጠየቁት? ወንድሞቹ  አንድ አካል መሆናቸውን ነው? መሆንን ነው ሚያሳይ ነው በእናንተ መረዳት መሠረት ዮሴፍና ወንድሞቹ አንድ አካል ናቸውን ?

እውነት ለሁሉ

30 Jan, 12:58


(አላሁ አክበር) ትልቁ ፅንፈኝነት!!

አንዳንዴ ሰዎች የምርም ሰው ናቸው እንዴ? ብዬ እንድጠይቅ እስኪያደርጉኝ ድረስ የፅንፈኝነት poweracheun ያንፀባርቃሉ፣ ከዚህም ባሻገር አምላኬ ክበር ይላሉ ይባስ በእነዚህን ፅንፈኛ ሰዎች የሚከብር አምላክ እንዳለ ሳስብ ደግሞ ይህ ሰው የሚገደልለት፣ሰው የሚወገርለት፣ አምላክ የምር እርሱ አምላክ ነው ወይስ አምላክ "የሚመስል" ሰይጣን? እላለሁ፣ በአንድ ወቅት ሙሥሊሞች በአረቡ አለም መፅሐፍ ቅዱስን የማቃጠል ዘመቻ ጀምረው ነበር ይህንን የተመለከተ (selwan) የተባለ ግለሰብ የአምላኩን ቃል ሲቃጠል በማየቱ እጅጉኑ መበሳጨትና ቁጭት ውስጥም ይገባል፣ እጅግ ስሜታዊ ከመሆኑ የተነሳ ይህን የህመም ስሜት ለምን እኔ ጋር ብቻ ይቀራል እናንተም ቅመሱት በሚል ስሜት የእስልምና መሠረት የሆነው (ቁርዓን)ን ያቃጥላል፣ ይህንን የተመለከቱ ሙስሊሞችም (ጅራፍ እራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሀል) አይነት ሰዎች ሆኑና ይህንን ሰው ማሳደድ ጀምረው ነበር፣ አሁን እየወጡ ባሉ መረጃዎች ደግሞ ይህ ግለሰብ እንደተገደለ ያሳያሉ፣ እናም ይህንን የሰሙ ሙሥሊሞች በደስታ እየፈነጩ ይገኛሉ ይህም በመሆኑ (አላሁ አክበር) በማለት ደስታቸውን እየገለጡ ነው፣ አላሁ አክበር እየተባለ ያለው ይህ ሰው በመገደሉ ነው የሰው ህይወት በመጥፋቱ የሚከብረው አምላክ ግን እርሱ ማነው? የምር እውነተኛው አምላክ የፈጠረውን ፍጥረት በመገደሉ፣በመወገሩ፣በመሰቃየቱ፣ ይከብራልን? በዚህ ተግባር የሚደሰቱና አምላኬ ሆይ ክበር ተመስገን የሚሉ ሰዎችስ የእውነት ሰው ናቸው? ይህ ለኔ ታላቅ ጥያቄ ፈጥሮብኛል፣ (selwan) ለታመንክለት አምላክ ይህም በነብያትና በሐዋርያት፣ የገለጠው ቃሉ ሲቃጠል ተቆጭተህ፣ ተመሳሳይ ተግባር መፈፀምህ ልክ ባይሆንም፣ካለህ መንፈሳዊ ቅንዓት የተነሳ ይህንን ተግብረህ ለክርስቶስ ቃል ተሟግተህ በአሳዳጆች ብትገደልም ክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራው እንደሚያስቀምጥህ አምናለሁ ነፍስህ ጌታ ይቀበላት፣ ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ። ማቴ፣10:28

እውነት ለሁሉ

30 Jan, 09:22


Sola Scriptura ወደ Solo Scriptura ሲወድቅ

Sola Scriptura ማለት የማይሳሳተው ብቸኛ ባለሥልጣን መጽሐፍ ቅዱስ ነው ሌሎች ባለሥልጣናት (የቤተክርስቲያን ትውፊት ፣ የቤተክርስቲያን አባቶች) ምንም ጠቃሚ ቢኾኑም ሊሳሳቱ ይችላሉ ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ መመዘን አለባቸው የሚል ሃሳብ ነው ይህም የቀዳምያኑ ሐዳስያን ታሪካዊ ፕሮቴስታንታዊ አቋም ነው። Solo Scriptura ደግሞ መጽሐፍ ቅዱስ ብቸኛ የማይሳሳት ብቻ ሳይኾን ብቸኛ ባልሥልጣን ነው ስለዚህ መጽሐፍ ቅዱስን ለመተርጎም የቤተክርስቲያን ትውፊትም ኾነ የአባቶች ትርጓሜ አያስፈልጉም ይላል።

እነዚህ ኹለቱ አቋሞች በtheory ደረጃ የተለያዩ ናቸው ነገር ግን ወደ practice ስናመጣቸው ወደ አንድነት መምጣታቸው አይቀርም ምክንያቱም Sola Scriptura ነው የምናምነው የሚሉ ሰዎች እነርሱ የማይቀበሏቸውን አስተምህሮዎች የቤተክርስቲያን አባቶች በስምምነት አስተምረው ሲያገኙት አባቶች ለመተርጎም አስፈላጊ ቢኾኑም አይሳሳቱም አላልንም ስለዚህ በዚህኛው ጉዳይ ተሳስተዋል ስለዚህ አልቀበልም ይላሉ። ታድያ በSolo Scriptura የሚያምኑትስ ከዚህ የተለየ ምን አደረጉ ከራሳቸው አስተምህሮ ጋር ሲገጥምላቸውማ እነርሱም ቢኾኑ የአባቶችን ትርጓሜ ልክ ነው ማለታቸው አይቀርም። ለምሳሌ አንድ ጊዜ ያጋጠመኝን ልንገራችሁ ልጁ በ Sola Scriptura ነው የማምነው አለኝ እሺ የአባቶች ትርጓሜ value አለው ብለህ የምታምን ከኾነ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ኹለተኛይቱ ሔዋን መኾኗን ከ2ተኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ያሉ አባቶች በአንድ ድምጽ አስተምረዋል ትቀበላለህ? ስለው "አልቀበልም መጽሐፍ ቅዱስ አይላትምና አባቶቹ ተሳስተዋል" አለኝ። አባቶች ከእናንተ ጋር ሲስማሙ ብቻማ መቀበል የአባቶች ትምህርት value አለው ብሎ ማመን ሳይኾን post fact justification ይባላል already የምታምኑበት የ reformers tradition አለ ከእዚህ tradition ጋር የሚስማሙ አባቶችን ትቀበላላችሁ የማይስማሙትን ደግሞ አትቀበሉም።

አባቶች በስምምነት ያስተማሩትን ከእናንተ tradition ጋር ስላልገጠመ ተሳስተዋል ብላችሁ የምትጥሉ ከኾነ ሌሎች ደግሞ ተነሥተው ከእነርሱ tradition ጋር ስላልገጠመ ብቻ "የኒቅያ አባቶች ተሳስተዋል ሥላሴ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አይደለም" ወይም "የቁስጥንጥንያ አባቶች ተሳስተዋል ጥምቀት ለኃጢአት ሥርየት አይደለም" ቢሉ እናንተ ካደረጋችሁት የተለየ ምን አደረጉ sola scriptura በአባቶች ትምህርት limit የሚበጅለት የቱ ጋር ነው? የአባቶችን መሳሳት እና አለመሳሳት በመጽሐፍ ቅዱስ ትርጓሜ የሚለየውስ ማነው?

እውነት ለሁሉ

30 Jan, 09:22


ከልብ የመነጨ ጥያቄ ለፕሮቴስታንቶች

ቤተክርስቲያን የሰዎች ስብስብ በመኾኗ ትሳሳታለች የማይሳሳት ብቸኛ ባለሥልጣን መጽሐፍ ቅዱስ ብቻ ነው ይባላል። ጥያቄዬ ቤተክርስቲያን የሰዎች ስብስብ እንደኾነች ኹሉ የትኛውም የፕሮቴታንት "አብያተ ክርስቲያናትም" ቢኾኑ የሰዎች ስብስብ በመኾናቸው የሚሳሳቱ ናቸው። ስለዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ መረዳት የቤተክርስቲያንን ትተን የእናንተን ለምን እንቀበል? ስህተት የሠራችው ቤተክርስቲያን ሳትኾን እናንተ ብትኾኑስ? የጥንት ቤተክርስቲያን አባቶች ትርጓሜን እንይ ትሉ ይኾናል በእናንተ Sola scriptura framework የራሳችሁን የግል መረዳት "የማይሳሳተው የመጽሐፍ ቅዱስ ሃሳብ" በሚል ሽፋን ከቤተክርስቲያን አባቶች ትርጓሜ በላይ በማድረጋችሁ የአባቶች ስምምነት ያለባቸውን አስተምህሮዎች ጭምር ተሳስተዋል በሚል assumption dismiss ታደርጋላችሁ። ለምሳሌ ቀዳምያኑ ሐዳስያን ጆን ካልቪንና ማርቲን ሉተር በunconditional election ያምናሉ ነገር ግን የጥንቷ ቤተክርስቲያን አባቶች በአንድ ድምጽ በ Conditional election ያምናሉ (And don't dare to quote Augustine here) ስለዚህ በዚህ አስተምህሮ መሠረት የተሳሳተው ማነው አብዛኞቹ የቤተክርስቲያን አባቶች ወይስ ሉተርና ካልቪን?

የአባቶች consensus ኖረውባቸው የማትቀበሏቸው አስተምህሮዎች አሉ? ካሉስ እኛ ተሳስተናል ከማለት ይልቅ ቤተክርስቲያን ተሳስታለች ወደ ማለት ለምን አደላችሁ?

እውነት ለሁሉ

29 Jan, 21:29


Collection
Sunan an-Nasa'i
Dar-us-Salam reference
Volume 5, Book 45, Hadith 4858
In-book reference
Book 45, Hadith 149
Reference
Hadith 4854

It was narrated from Abi Bakr bin Muhammad bin 'Amr bin Hazm, from his father, from his grandfather, that:

the Messenger of Allah wrote a letter to the people of Yemen included in which were the rules of inheritance, the sunan and the (rules concerning) blood money. He sent it with 'Amr bin Hazm and it was read to the people of Yemen. This is a copy of it. And he mentioned something similar, except that he said: "And for one eye, half the Diyah must be paid; for one hand, half thediyah must be paid; for one foot, half the diyah must be paid. " (Daif)

أَخْبَرَنَا الْهَيْثَمُ بْنُ مَرْوَانَ بْنِ الْهَيْثَمِ بْنِ عِمْرَانَ الْعَنْسِيُّ، قَالَ حَدَّثَنَا مُحَمَّدُ بْنُ بَكَّارِ بْنِ بِلاَلٍ، قَالَ حَدَّثَنَا يَحْيَى، قَالَ حَدَّثَنَا سُلَيْمَانُ بْنُ أَرْقَمَ، قَالَ حَدَّثَنِي الزُّهْرِيُّ، عَنْ أَبِي بَكْرِ بْنِ مُحَمَّدِ بْنِ عَمْرِو بْنِ حَزْمٍ، عَنْ أَبِيهِ، عَنْ جَدِّهِ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم كَتَبَ إِلَى أَهْلِ الْيَمَنِ بِكِتَابٍ فِيهِ الْفَرَائِضُ وَالسُّنَنُ وَالدِّيَاتُ وَبَعَثَ بِهِ مَعَ عَمْرِو بْنِ حَزْمٍ فَقُرِئَ عَلَى أَهْلِ الْيَمَنِ هَذِهِ نُسْخَتُهُ فَذَكَرَ مِثْلَهُ إِلاَّ أَنَّهُ قَالَ ‏

"‏ وَفِي الْعَيْنِ الْوَاحِدَةِ نِصْفُ الدِّيَةِ وَفِي الْيَدِ الْوَاحِدَةِ نِصْفُ الدِّيَةِ وَفِي الرِّجْلِ الْوَاحِدَةِ نِصْفُ الدِّيَةِ ‏"

‏ ‏.‏ قَالَ أَبُو عَبْدِ الرَّحْمَنِ وَهَذَا أَشْبَهُ بِالصَّوَابِ وَاللَّهُ أَعْلَمُ وَسُلَيْمَانُ بْنُ أَرْقَمَ مَتْرُوكُ الْحَدِيثِ وَقَدْ رَوَى هَذَا الْحَدِيثَ يُونُسُ عَنِ الزُّهْرِيِّ مُرْسَلاً ‏.‏



ሙሀመድ መጻፍ ይችላል

the Messenger of Allah wrote a letter to the people of Yemen ለየመኔች መሀመድ እንደጻፈ ከላይ ሀዲሱ የመጀመርያ ጹሁፍ ላይ አለ መሀመድ መጻፍ አይችልም ሲሉን የነበረው ውሸት ነው ማለት ነው 😁

እውነት ለሁሉ

29 Jan, 08:11


የቀጠለ

ወሒድ
3. ሃይማኖተ-አበው ዘጎርጎርዮስ 35:6
ጎርጎርዮስም አለ፦ “ስጋ ስለሆነ ፍጡር ይባላል”

ምላሽ 
ወሒድ ጥቅሶችን በመቆራረጥ ለራሱ ሀሳብ ለማመቻቸት እየጣረ ነው። ሙሉ ጥቅሱ እንዲህ የሚል ነው።

"ዳግመኛም ባህሪያችንን ተዋሕዶ ሰው ስለሆነ (ዘኮነ ሥጋ ወኀደረ ላእሌነ) ሰው (ፍጡረ) ይባላል። እርሱ ሰው በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር በሥጋ እንደ ታየ በሥራው ጌትነቱን ገለ

ጠ፣ እርሱ አምላክ ወልድ ወሕድ በአባቱ ዕሪና ያለ ነው።" 

እንግዲህ በጥቅሱ እንደ ተገለጸው ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ የተገለጠ እግዚአብሔር ነው። ነገር ግን የተፈጠረ ባህሪያችንን ተዋህዶ ሰው ስለሆነ ስለ ተዋሐደው ሥጋ ሲናገር (ከተዋህዶ በፊት ስለ ነበረው ሥጋ ሲናገር) ፍጡር ይባላል አለ። መክንያቱም የተዋሐደው የእኛ ባህርይ ፍጡር ነውና። ይህ ማለት ግን ከተዋሐዶ በኃላ በሥጋው ፍጡር ነው ማለት አይደለም። እርሱ ጥንት የሌለው ፈጣሪ ሲሆን የተዋሐደው ሥጋ ግን ጥንት መገኛ ያለው ፍጡር ነው።

"በተገዥ የአዳም ባሕርይም በሥጋ የሰውነትን ሥራ ሠራ፣ጥንት የሌለው እርሱ ያለ መለወጥ ንጽህት ከምትሆን ከቅድስት ድንግል ማርያም የነሣውን ጥንት መገኛ ያለውን የሥጋን ባህርይ በተለየ አካሉ ተዋሐደ" ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎሪዮስ35÷12

ወሒድ
“ፍጡረ” ማለት “ፍጡር” ማለት ነው። አንዱ እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃሉ ከዳዊት ዘር ለእስራኤል መድኃኒትን ኢየሱስን ካለመኖር ወደ መኖር አመጣ፤ ይህም የተስፋ ቃል ኢየሱስ በማህፀን የተፈጠረ ፍጡር መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳያል፦
ሐዋ ሥራ 13፥23 ከዚህም ሰው ዘር እግዚአብሔር እንደ ተስፋው ቃል ለእስራኤል መድኃኒትን እርሱም *ኢየሱስን አመጣ።
ኢሳይያስ 49፥5-6 ያዕቆብን ወደ እርሱ እንድመልስ እስራኤልንም ወደ እርሱ እንድሰበስብ ባሪያ እሆነው ዘንድ ከማኅፀን ጀምሮ የሠራኝ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፡— እርሱም፡— የያዕቆብን ነገዶች እንድታስነሣ ከእስራኤልም የዳኑትን እንድትመልስ ባሪያዬ ትሆን ዘንድ እጅግ ቀላል ነገር ነውና እስከ ምድር ዳር ድረስ መድኃኒት ትሆን ዘንድ ለአሕዛብ ብርሃን አድርጌ ሰጥቼሃለሁ፥ ይላል።

ምላሽ
ከማሕጸነ ማርያም በፊት ህልውና እንደ ነበረው እራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌል ደጋግሞ ነግሮናል።

" ከአብ ወጥቼ ወደ ዓለም መጥቻለሁ፤ ደግሞ ዓለምን እተወዋለሁ ወደ አብም እሄዳለሁ።"
(የዮሐንስ ወንጌል 16:28)

" ኢየሱስም። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ አብርሃም ሳይወለድ እኔ አለሁ አላቸው።"
(የዮሐንስ ወንጌል 8:58)

ይህ ከሆነ በማህጸን ሰራኸኝ የሚለው ስለ ምንድነው ከተባለ ስለ ተዋሃደው ሥጋ ነው። በማህጸን ውስጥ የተዋሃደው ሥጋ  በእግዚአብሔር የተፈጠረ ነው። 

" ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ። መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ፤"
(ወደ ዕብራውያን 10:5)

ይህ በድንግል ማርያም ማህጸን ከእሷ ተወስዶ የተሰራው(የተዘጋጀው) ሥጋ የተፈጠረ ነው። እሱ ያንን የተፈጠረ ሥጋ ስለ ተዋሐደ በማህጸን የሰራከኸኝ አለ። እስቲ ማስረጃ ይሆንልኛል ብሎ የጠቀሰው አባት እንዴት እንደ ተረጎመው እንይ!

ወሒድ 
1.ሃይማኖተ-አበው ዘቄርሎስ 76:19
ቄርሎስምአለ፦

“ዳግመኛም መድኅን ክርስቶስ ከድንግል ስለመወለዱ በኢሳይያስ አፍ “ብዙ ሥራ እሠራ ዘንድ የያዕቆብንም ወገን አጸና
ዘንድ አስራኤልንም አንድ አደርግ ዘንድ በማሕጸን ተፈጠርኩ አለ”

ምላሽ
ቅዱስ ቄርሎስ በማህጸን ሰራኝ/ፈጠረኝ የሚለውን እንዴት እንደ ተረጎመው ከእዛው ከቅዱስ ቄርሎስ ንግግር እንመልከት።

"የምትናገር የምታውቅ ነፍስ ያለችው ሥጋን ሊዋሐደው ከድንግል ፈጠረ" ሃይማኖተ አበው ዘቄርሎስ 76÷27

"በኃለ የተገኘን ሥጋ ሊዋሐደው ከዳዊት ባሕርይ እርሱ ፈጠረ እንደ ተጻፈ ከሦስቱ አካላት አንዱን አደረገው"  ሃይማኖተ አበው ዘቄርሎስ77÷2

ቅዱስ ቄርሎስ ደጋግሞ እንደ ተናገረው  አካላዊ ቃል የተዋሃደው የተፈጠረን ሥጋን ነው። በመፍጠር ከአባቱ ጋር አንድ ስለሆነ በነቢያት ሥጋን አዘጋጀህልኝ፣ በማህጸን ሰራኝ ያለውን እሱ እራሱ ኢየሱስ የሚዋሐደውን ሥጋ እንደ ፈጠረ ገለጸ። ወሒድም ሆኑ ሌሎች ሙስሊሞች በመለኮትና በሥጋ መካከል ስለተደረገው ተዋሕዶ በሃይማኖተ አበው መጽሐፍ የተገለጸውን ሙሉ ሀሳብ እንዲያዩ ግብዣዬ ነው።

ማጠቃለያ
ወሒድ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ፈጣሪነት ደጋግሞ ከሚናገረው መጽሐፍ ጠቅሶ መናገሩ እራሱን አጣብቂኝ ውስጥ እየከተተ ነው። ስለ ተዋሐደው ሥጋ የተነገሩትን ጥቅሶችም አስቀድሞ ከነበረው መለኮታዊ ህልውና ጋር ተምታቶበት ይዳክራል። እባክህን ጥቅስ እየቆራረጥክ አንተም ተወዛግበክ ሰው አታወዛግብ። እግዚአብሔር ልቦናህን ያብራልህ!

   (ኡስታዝ ወሒድ) መጀመሪያ ክርስትናን ለመተቸት የክርስትና ትምህርት ምን እንደሆነ መረዳት አለብህ አንተ ያለ ምንም እውቀት በጭላንጭል ድፍረት የምትጓዝ ሰው ሆይ አንብብ አንብብ

   ወሰላሙ አለይኩም🫡

እውነት ለሁሉ

28 Jan, 22:06


ስግደት ሰው በአምላኩ ፊት አምልኮትን በታላቅ ሰው ፊት አክብሮትን ለመግለጽ ሊጎነበስ ራስን ማዘንበል አጽንኖ በጉልበት መንበርከክ አስተብርኮ ወይም በግባሩ በመሬት ላይ ሊወድቅ ይችላል

የኢትዮጵያ መጽሀፍ ቅዱስ ማህበር
የመጽሀፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ገጽ84

እውነት ለሁሉ

28 Jan, 19:19


እንኳን አደረሳችኹ የእመቤታችን ምልጃና በረከት ይጽናብን....!!
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!!
🥰🥰🥰

እውነት ለሁሉ

28 Jan, 08:11


ሃይማኖተ አበው ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጡር ነው ይላልን? Well  እንግዲህ

ወሒድ ዑመር ሃይማኖተ አበው  የተባለው የቤተክርስቲያን መጽሐፍ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጡር ነው ይላል ብሎ ትልቅ የቅጥፈት ፅሁፍ ፅፎ አስነብቦናል። ሃይማኖተ አበው የተባለው መጽሐፍ በይበልጥ ምሥጢረ ሥላሴን እና ምሥጥረ ሥጋዌን (ነገረ-ክርስቶስን) የሚያስረዳ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ቀደምት የቤተክርስቲያን አባቶች( Early Church Fathers) ለመናፍቃን እና ለከሃድያን የሰጡትን ምላሾች እና ተግሳጾችን አሰባስቦ የያዘ ነው። እስቲ የወሒድ የስህተት ሀሳቦችን እንመልከት!

ወሒድ
"የተፈጠረ ነገር ሁሉ ላይወለድ ይችላል፥ ለምሳሌ መላእክት ተፈጥረዋል ግን አልተወለዱም። ግን የተወለደ ነገር ሁሉ ከመወለዱ በፊት በማኅጸን ይፈጠራል። ኢየሱስ ማርያም ማህፀን ውስጥ መፈጠሩን በተለይ የክርስትና የዐቂዳህ መጽሐፍ የሆነው ሃይማኖተ-አበው ኢየሱስ ከመወለዱ በፊት በማህጸን ውስጥ የተፈጠረ “ፍጡር” ነው ይላል፦"

ምላሽ
ወሒድ "የተወለደ ሁሉ አስቀድሞ በማህጸን ይፈጠራል" በማለት የኢየሱስ ሕልውና የጀመረው በድንግል ማርያም ማህጸን ውስጥ እንደሆነ አድርጎ ያስቀምጣል። ኢየሱስ በማህጸን ተፈጠረ የሚለው የወሒድ ሀሳብ የኢየሱስ ሕልውና በማህጸን የተጀመረ እንደሆነ የሚናገር ነው። መክንያቱም መፈጠር ማለት ካለ መኖር ወደ መኖር መምጣት ነው።ከዚያም ከሃይማኖተ አበው መጽሐፍ ማስረጃ ብሎ የተወሰኑ ጥቅሶችን ጠቅሷል። ወሒድ ከሃይማኖተ አበው እራሱ ሲጠቅስ በትክክል አይጠቅስም። ለምን እንደዚህ እንዳልኩ ከታች እንመለከተዋለን። ወሒድ ወደ ጠቀሳቸው ጥቅሶች ከማለፋችን በፊት እሱ እራሱ የጠቀሳቸው አባቶች ውስጥ ስለ ኢየሱስ ቅድመ ህልውና(ከማህጸን በፊት ስለመኖሩ) የተናገሯቸውን እንይ!
1. ወሒድ መጠሊጎን ጠቀሰው ብሎ ከሃይማኖተ አበው ምእራፍ 44÷3 ጠቅሷል። ነገር ግን ሃይማኖተ አበው ምእራፍ 44÷3 ሃይማኖተ አበው ዘመጠሊጎን ሳይሆን ዘአዮክንድዮስ ነው።  አዮክንድዮስ የተናገረውን መጠሊጎን ተናገረ ብሎ የተሳሳተ መረጃ ሰጥቷል። ስህተቱ እንዳለ ሆኖ እሱ ከጠቀሰበት ምእራፍ 44 አዮክንድዮስ ኢየሱስ ከማህጸነ ማርያም በፊት ህልውና እንደ ነበረው የተናገረውን እንይ!
"የእግዚአብሔር ቃል ከሰማይ በወረደ ጊዜ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ማህጸን በአደረ ጊዜ..." ሃይማኖተ አበው ዘአዮክንድዮስ 44÷2
በዚህ ጥቅስ ላይ የእግዚአብሔር ቃል ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ድንግል ማርያም ማህጸን ከመምጣቱ በፊት በሰማይት እንደኖረ በግልጽ ተቀምጧል።
2. ወሒድ ከቄርሎስ መልክት ጠቅሷል። የጠቀሰው ቄርሎስ የተናገረውን ቢሆንም የጠቀሰው ክፍል ግን ሃይማኖቱ አበው ዘቄርሎስ አይደለም የሚባለው። ሃይማኖተ አበው ዘቄርሎስ እራሱን የቻለ ሌላ ክፍል ነው። ምእራፍ 124 ሃይማኖተ አበው ስምዓት ተብሎ ሲጠራ ክፍሉ የተለያዩ ሊቃውንት የተናገሩትን በአንድ ላይ አሰባስቦ የያዘ ክፍል ነው። ወሒድ የመጽሐፉን ክፍል ስም እንኳን በአግባቡ ሳያውቀው ከመጽሐፉ ለመጥቀስ መዳፈሩ ይገርማል። ኢየሱስ ከማህጸነ ማርያም በፊት እንደነበረ የሚናገር ጥቅስ እሱ እራሱ ከጠቀሰው የቅዱስ ቄርሎስ መልእክት ከሚገኝበት ሃይማኖተ አበው ስምዓት እንመልከት።
" እሱ የባህርይ አምላክ እንደሆነ፣ በባህርዩን ፍጥረትን ሁሉ ፈጥሮ መግዛት ገንዘቡ እንደሆነ፣ የተገዥ የአዳምን ባሕርይ ቢነሣም ከፍጥረቱ ሁሉ በላይ እንደሆነ፣ ፍጹም ሰው በሆነ ጊዜም  ከሰው ጋር አንድ እንደሆነ እናምናለን" ሃይማኖተ አበው ስምዓት124÷18

በጥቅሱ በግልጽ እንደ ተቀመጠው ፍጥረታትን ፈጥሮ የሚገዛቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ፍጥረታትን የፈጠረው እሱ ከሆነ ሕልውናው በማህጸነ ማርያም የተጀመረ ነው (በማህጸን የተፈጠረ ነው) የሚለው የወሒድ ቅዠት ነው።

3. ወሒድ በሶስተኛ ደረጃ የጠቀሰው ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎሪዮስን ነው። እስቲ ጎርጎሪያስ ኢየሱስ ክርስቶስ ከማህጸነ ማርያም በፊት በአምላክነት እንደ ነበረ የተናገረበት ጥቅስ እንመልከት።

"ክርስቶስ ማለት ፈጣሪና ፍጡር አንድ አካል አንድ ባሕርይ በመሆን አንድ ሆነ ማለት ነው። ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ለዘላለሙ የሚኖር ያለውን ሁሉ የፈጠረ እርሱ ነውና ስለ እርሱ ስንናገር ያልተፈጠረ ነው እንላለን" ሃይማኖተ አበው ዘጎርጎሪዮስ 35÷2

ወሒድ ማስረጃ ይሆኑልኛል ብሎ የተጠቀሳቸው አባቶች በሙሉ በአንድ ላይ ተስማምተው ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ፈጣሪነት፣ አለም ሳይፈጠር በመለኮቱ ስለ መኖሩ ይመሰክራሉ። ይህ ከሆነ ወሒድ ማስረጃ ይሆኑልኛል ብሎ የጠቀሳቸው ምንድናቸው? ወደ ሚለው ሀሳብ እንምጣ።

በመጀመሪያ አንድ መታወቅ ያለበት በሃይማኖተ አበው ውስጥ ኢየሱስ ፍጡር ነው የሚል በፍጹም የለም። ወሒድም እንደዚህ የሚል ማስረጃ አምጥቶ መሞገት ከቻለ ይሞግተን። ወሒድ ሃይማኖተ አበው ኢየሱስ ፍጡር ይላል ለማለት የጠቀሳቸው ጥቅሶች ሲመዘኑ:-

ወሒድ
1. ሃይማኖተ-አበው ዘመጠሊጎን 44፥3
“እርሱ ሥጋውን በድንግል ማሕፀን ፈጠረ፤ ሥጋውን በመፍጠር ማንም አጋዥ አልሆነውም፤ እርሱ እራሱ ፈጠረው እንጂ”

ምላሽ
በመሠረቱ ከላይ እንደ ገለጽኩት ይህን ጥቅስ የተናገረው መጠሊጎን ሳይሆን አዮክንድዮስ ነው። ወሒድ ስሙን እንኳን በአግባቡ ሳያጣራ ነው ከመጽሐፉ የጠቀሰው። አንባቢያን ኢየሱስ ፍጡር ነው የሚል ወሒድ በጠቀሰው ላይ አለ? በፍጹም የለም። እንዲያውም የኢየሱስ ፈጣሪነትን ነው የሚናገረው።

"እርሱም ሥጋውን በድንግል ማሕፀን ፈጠረ" ብሎ የሚዋሃደውን ሥጋ አስቀድሞ በድንግል ማርያም ማህጸን እንዳዘጋጀ ይነግረናል። " እርሱም" የተባለው ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ የምናውቀው ከላይ ጀምሮ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እያወራ በመምጣቱ ነው። በተጨማሪም "ሥጋውን" ብሎ ለኢየሱስ ክርስቶስ ባለቤትነት ሰጥቷል። ሥጋን የተዋሃደው ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ወሒድ እራሱ በጠቀሰው ጥቅስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ፈጣሪነት ይመሰክራል።
   
ወሒድ 
2. ሃይማኖተ-አበው ዘቄርሎስ 124:19
ቄርሎስም አለ፦
“ከሴት በሥጋ ስለተወለደ ፍጡር ነው እንላለን”

ምላሽ
ቅዱስ ቄርሎስ "በሥጋ ስለተወለደ" ያለውን እናስተውል። ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ የተዋሃደው የፍጡርን ሥጋ ነው። ለዚህም ከተዋህዶ በፊት ስለ ነበረው ሥጋ ሲናገር ፍጡር ነው እንላለን አለ።  በተጨማሪም በሥጋው የሚለው ቃል በመለኮቱ ፍጡርነት እንደ ሌለበት ያሳያል። ወሒድ ጥቅሱን ቆርጦ አቀረበው እንጂ ሙሉ ጥቅሱ እንዲህ ነው የሚለው:-

"ንብሎ ፈጣሪ በእንተ ከመ ውእቱ አምላክ ወእግዚአብሔር፣ ንብሎ ፍጡረ እስመ ውእቱ ወዓዲመ ንብሎ ፍጡረ እስመ ውእቱ ተወልደ በሥጋ እምብእሲት---አምላክ እግዚአብሔር ስለሆነ ፈጣሪ  እንለዋለን፣ ወዲህም ከድንግል በሥጋ ስለ ተወለደ ሰው(ፍጡረ) እንለዋለን"!  

ወሒድ ፈጣሪ እንለዋለን የሚለውን ቆርጦ አውጥቶ በሥጋ ከድንግል ስለ ተወለደ እና የፍጡርን ስጋ ስለ ተዋሃደ " ንብሎ ፍጡረ" የሚውን ብቻ ወስዶ ለማወዛገብ ይሞክራል። ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ብሎ ለሚያምን ይህ ሀሳብ ግልጽ ነው።

    ይቀጥላል

እውነት ለሁሉ

28 Jan, 07:20


አምልኮና ለፍጡራን የሚቀርብ አገልግሎትን ለመለየት የቅዱስ አውግስጢኖስን The City of God (Book X) አንብቡ በዛውም እንዴት ፕሮቴስታንቶች (ቅዱስ ቁርባን መሥዋዕት አይደለም የሚሉት) አምላክን እንደማያመልኩ ትረዳላችሁ።

Chapter 1

For this is the worship which is due to the Divinity, or, to speak more accurately, to the Deity; and, to express this worship in a single word as there does not occur to me any Latin term sufficiently exact, I shall avail myself, whenever necessary, of a Greek word. Λατρεία, whenever it occurs in Scripture, is rendered by the word service. But that service which is due to men, and in reference to which the apostle writes that servants must be subject to their own masters, Ephesians 6:5 is usually designated by another word in Greek, whereas the service which is paid to God alone by worship, is always, or almost always, called λατρεία in the usage of those who wrote from the divine oracles. 

Chapter 6

Thus a true sacrifice is every work which is done that we may be united to God in holy fellowship, and which has a reference to that supreme good and end in which alone we can be truly blessed. And therefore even the mercy we show to men, if it is not shown for God's sake, is not a sacrifice. For, though made or offered by man, sacrifice is a divine thing, as those who called it sacrifice meant to indicate. Thus man himself, consecrated in the name of God, and vowed to God, is a sacrifice in so far as he dies to the world that he may live to God. For this is a part of that mercy which each man shows to himself; as it is written, Have mercy on your soul by pleasing God. Sirach 30:24 Our body, too, as a sacrifice when we chasten it by temperance, if we do so as we ought, for God's sake, that we may not yield our members instruments of unrighteousness unto sin, but instruments of righteousness unto God. 

it follows that the whole redeemed city, that is to say, the congregation or community of the saints, is offered to God as our sacrifice through the great High Priest, who offered Himself to God in His passion for us, that we might be members of this glorious head, according to the form of a servant. For it was this form He offered, in this He was offered, because it is according to it He is Mediator, in this He is our Priest, in this the Sacrifice.

This is the sacrifice of Christians: we, being many, are one body in Christ. And this also is the sacrifice which the Church continually celebrates in the sacrament of the altar, known to the faithful, in which she teaches that she herself is offered in the offering she makes to God.

Chapter 20

And hence that true Mediator, in so far as, by assuming the form of a servant, He became the Mediator between God and men, the man Christ Jesus, though in the form of God He received sacrifice together with the Father, with whom He is one God, yet in the form of a servant He chose rather to be than to receive a sacrifice, that not even by this instance any one might have occasion to suppose that sacrifice should be rendered to any creature. Thus He is both the Priest who offers and the Sacrifice offered. And He designed that there should be a daily sign of this in the sacrifice of the Church, which, being His body, learns to offer herself through Him. Of this true Sacrifice the ancient sacrifices of the saints were the various and numerous signs; and it was thus variously figured, just as one thing is signified by a variety of words, that there may be less weariness when we speak of it much. To this supreme and true sacrifice all false sacrifices have given place.

(ኪዳን ዘኢየሱስ)

እውነት ለሁሉ

27 Jan, 17:42


https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!!
🥰🥰🥰

እውነት ለሁሉ

27 Jan, 09:11


ነገረ ድህነት ንጽጽራዊ ዕይታ

ክርስትና 🆚 እስልምና

@እፎይ
@ታላቁ
@ጰላዲዮስ

እውነት ለሁሉ

26 Jan, 20:38


ሰበር ዜና ስለመጋጨት ከኡስታዞች
እስከ ዛሬ ድረስ መጽሐፍ ቅዱስ ይጋጫል ብለው ቢመለስላቸው አልሰማ ብለው ሲሞግቱ ሚውሉት ሙስሊሞች

በራሳቸው ቁርአን ሲመጣ ሁለት የተለያየ ሚቃረን ቃላት መኖሩ ተጋጨ አያስብልም 🤪
እናሳ ተጋጨ ለመባል ሁለት የተለያዩ ቃላት መኖራቸው ሳይሆን የእኔ መስፈርት ብዬ ማስቀምጠው ብሎ ሶስት ሀሳቦችን ጠቀሰ ለመጋጨት መስፈርት ሚሆነው ብሎ 😁

ከዚህ እስላም አቃቤ ነኝ ከሚለው ምን እንይዛለን እንደ ልጁ የራሴ መስፈርት ብሎ ሶስት ከጠቀሰ
ሌላው ከዛ በላይ ሊጠቅስ ይችላል እንደራሱ መስፈርት ስለሆነ ሶስት የጠቀሰው

እኛም ሶስት ወይም ከዛ በላይ መስፈርት አውጥተን በዛ እንደሆነ እንጂ እንደ እስከ ዛሬው ሁለት የተለያዩ ቃላት አምጥቶ ተጋጨ ማለት ተጋጨ አያስብልም ኡስታዛችሁን ስሙ ከዚ በኃላ ጥቅስ መዞ ተጋጨ ማለት ድሮ ቀረ 😁

እውነት ለሁሉ

26 Jan, 10:32


ሃይማኖተ አበው ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጡር ነው ይላልን።? ወሒድ ዑመር ሃይማኖተ አበው  የተባለው የቤተክርስቲያን መጽሐፍ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍጡር ነው ይላል ብሎ ትልቅ የቅጥፈት ፅሁፍ ፅፎ አስነብቦናል። ሃይማኖተ አበው የተባለው መጽሐፍ በይበልጥ ምሥጢረ ሥላሴን እና ምሥጥረ ሥጋዌን (ነገረ-ክርስቶስን) የሚያስረዳ መጽሐፍ ነው። መጽሐፉ ቀደምት የቤተክርስቲያን አባቶች( Early Church Fathers) ለመናፍቃን እና ለከሃድያን የሰጡትን ምላሾች እና ተግሳጾችን አሰባስቦ የያዘ ነው። እስቲ የወሒድ የስህተት ሀሳቦች ሰሞኑን እንዳስሳለን መቼስ ፈርዶብናል💀

እውነት ለሁሉ

26 Jan, 10:11


ዕቅበተ እምነት

ዕቅበተ ማለት ቃሉ የግዕዝ ሲሆን መጠበቅ፣ ጥበቃ የሚል የአማርኛ ትርጉም አለው።(ኪዳነወልድ ክፍሌ መፅሀፈ ሰዋሰው ወግስ መዝገበ ቃላት ሐዲስ ገፅ.705)እምነት የሚለውም ሃይማኖትን እምነትን ማለት ነው። ዕቅበተ እምነት ማለት የእምነት ጥበቃ ማለት ነው። 
ዕቅበተ እምነትን የሚተገብረው ሰውም ዐቃቤ እምነት ይሰኛል። ዐቅበተ እምነትን በህብረት የሚሰሩ ከሆኑም ዐቃቢያነ እምነት ይሰኛሉ።
.
እምነትየሚጠበቀውም ከሃሳውያን መምህራን ከሃሳውያን የፍልስፍና አራማጆች ወደ ቤተ ክርስቲያን የሀሰት ትምህርትን ሲያስገቡ መካለከልና ለእነሱም መልስን መስጠት ነው።
በመፅሀፍ ቅዱሳችን አንድ ታሪክ አለ እርሱም በሐውርያት ስራ ምዕራፍ 17 ላይ የሚገኝ ነው። ብርሃነ አለም ቅዱስ ጳውሎስ ከአይሁድ ጋር ወይይቶችን ያደርግ ነበረ ስለ ክርስቶስ ኢየሱስም መሲህነት ስለ ሀጢያታችን በቀራኒዮ መሰቀል ሞቶም ስለመነሳቱ ህያው አምላክ ለመሆኑም ይመስክር ነበረ። ምክንያቱም በዚያ ዘመን አይሁዶች ብዙ ክርስትናን ለማፈራረስ ይጥሩ ስለነበረ ነው፤ እርሱ ግን ብሉያትን እያጣቀሰ ይመልስላቸው ነበረ።

የዐቅበተ እምነት ታሪኮች በታላላቅ ጉባኤያት
➫የኒቅያ ጉባኤ፦ ይህ ጉባኤ የተካሄደው በ318 ዓመተ ምህረት ወልድን ፍጡር ነው ብሎ የስህተት ትምህርት ያሰራጨውን አርዮስን በመፅሀፍ ቅዱስ መሰረት መልስ የተሰጠበትና፤ ከጉባኤያትም ሁሉ የላቀ ነው በጉባኤውም 318 የበቁ የነቁ የሃዋርያትን ፈለግ በተከተሉ ቅዱሳን አባቶች የእምነት ጠበቆች  የተገኙበት ነው። ከእነሱም ልቆ የነበረው ዐቃቤ እምነትም በእለቱ ሊቀ ዲያቆን የነበረው ቅዱስ አትናቴዎስ ነበር።
 ➫የቁስጥንጥንያ ጉባኤ፦ ይህ ጉባኤ የተካሄደው በ381 ዓም በ150 ኤጲስቆጶሳት የተካሄደ ሲሆን ለዚህ ጉባኤ መካሄድ በዋናነት
➾መንፈስ ቅዱስ ሕጹጽ ነው(ፍጡርነው)ያለውን የመቅዶንዮስ የሀሰት ትምህርት 
➾ቃለ እግዚአብሔር የተዋሃደው ስጋን እንጅ ነፍስን አይደልም ላለው ለአቡሊናሪዮስ
➾እንዲሁም ቃለ እግዚአብሔር የተዋሃደው የአዳምን ስጋ ሳይሆን፤ ሌላ በቅድምና የነበረን ስጋ ነው ለሚሉ መናፍቃን ነበረ። ለእነዚህም መናፍቃን ተገቢውን መልስ በመስጠት ክርስትና ሃይማኖትን ከዚህ አድርሰውልናል በዚህም ጉባኤ አንድ ታላቅ ዐቃቤ እምነት ተነስቷል እሱም ጎርጎርዮስ ዘኢንዙናዚ(ነባቤመለኮት)
➫የኤፌሶንጉባኤ፦ በዚህ ጉባኤ በሊቀ ጳጳሱ በንስጥሮስ ይስፋፋ የነበረውን የሁለት አካል ትምህርት ነበረ ይህም የአብ ልጅና የማርያም ልጅ የተለያዩ ሁለት አካላት ናቸው፣ ድንግል ማርያም እመ አምላክ አትባልም እርሷ የወለደችው ዕሩቅ ብዕሲ ነው ቡሃላም በጥምቀት ቃል አደረበት"" በማለት በስልጣኑ ተመክቶ ይህን የስህተት ትምህርቱን ሲያስፋፋ 200 የሚሆኑ ደጋግ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ጉባኤን በ431  ዓም አሰናዱ ይህንም የስህተት ትምህርቱን መፅሀፍ ቅዱስን መሰረት አድርገው ውድቅ አደረጉት!
በዚህጉባኤም ለክህደታቸው መልስ በመስጠት ቅዱስ ቄርሎስ የላቀውን ድርሻ ይይዛል።

እንግዲህ የሃይማኖት ጥበቃ ከጥንት ከሃዋርያት ጀምሮ በሊቃውንት አልፎ ከዚህ ካለንበት ዘመን የደረሰ ነው። በዘመናችንም ለቁጥር የሚያታክቱ ከእውነተኛው ወንጌል ከእውነተኛውም የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ የወጡ ትምህርቶች ይደመጣሉ። እነሆ እኛም ልክ እንደአባቶቻችን ብራናን ፍቀን ቀለም በጥብጠን ብዕር ቀርፀን ጉባኤን ሰርተን ለሃሳውያን መልስ ለመስጠት የእነሱን ያህል ፀጋው ባይኖረንም እንደ አቅማችን በዚሁ በማህበራዊ ሚዲያ መልስ ለመስጠት እነሆ ጀምረናል።
መልካም የአብሮነት ጊዜ!
.
በእናንተስላለ ተስፋ ምክንያትን ለሚጠይቁዋችሁ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃችሁ ሁኑ፥ ነገር ግን በየዋህነትና በፍርሃት ይሁን።
1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 3 :15 እንደሚለን!
.
መልካም ንባብ!
ምንጭ ዕቅበተእምነት ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ

እውነት ለሁሉ

26 Jan, 10:00


ለእግዚአብሔር ምስጋናን እና ቅዳሴን በየዕለቱ ፈጽሞ ሳያቋርጥ የሚያቀርብ ሰው በሰይጣን ተፈትኖ ከመውደቅ መንፈስ ቅዱስ ይሰውረዋል፤ በድንገት ከባድ ፈተና ገጥሞት ቢወድቅ እንኳ መንፈስ ቅዱስ አጸጽቶ ወደ እውነተኛ ንሥሐ ይመልሰዋል።                                                   ቅዱስ ሳዊሮስ ዘእስሙናይን፣ መጽሐፈ ሳዊሮስ ዘእስሙናይን፣ ድርሳን 4።

እውነት ለሁሉ

26 Jan, 08:38


https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!!

እውነት ለሁሉ

23 Jan, 09:36


ሐዋርያት የቆረቡት ከምግብ በኋላ ምሽት ላይ ሆኖ ሳለ ለምን እኛ ቅዱስ ቁርባን ለመቀበል እንጾማለን?

የዚህ ጥያቄ መንፈስ “ከሐዋርያት ጋር ፉክክር” ያለ ያስመስላል፡፡ በመሠረቱ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን እንደሚያስተምሩት ‹‹የጸሎተ ሐሙስ ዕለት አስቀድመው የፋሲካውን በግ ከበሉ በኋላ በግብር አምላካዊ አስቀድመው የበሉትን አጥፍቶ ለበረከት ካመጡለት ከኅብስቱና ከወይኑ ከፍሎ “ይህ ሥጋዬ ነው፣ ይህ ደሜ ነው” ብሎ ለውጦ ትኩስ ሥጋ ትኩስ ደም አድረጎ አቁርቧቸዋል›› በማለት አመስጥረው ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው አድርጎ እንደሰጠን አስተምረውናል፡፡ በወንጌል እንደተጻፈ ቅዱስ ዮሴፍ ዘአርማትያስ ጌታችን እንዲቀበርበት የመረጠው መቃብር “በውስጡ ሰው ያልተቀበረበት አዲስ መቃብር ነበር፡፡” (ዮሐ. 19፡41) እኛ ደግሞ ስንቆርብ የምንቀበለው ዮሴፍና ኒቆዲሞስ እንደገነዙት ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደውን የክርስቶስን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደም እንደሆነ ቅድስት ቤተክርስቲያን ታስተምራለች፡፡ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በአዲስ መቃብር ጌታችንን እንደቀበሩት ከቅዱስ ቁርባን የሚቀበሉ ምዕመናንንም አፋቸውን ምሬት እስኪሰማቸው (ሆዳቸው ባዶ እስኪሆን) ለ18 ሰዓታት በመፆም እንዲቆርቡ ቅዱሳን አባቶቻችን ሥርዓትን ደንግገውልናል፡፡

እውነት ለሁሉ

23 Jan, 07:42


እግዚአብሔር የባሕርዩንና የሥልጣኑን ገፅታ በፍጥረታዊው ዓለም ውስጥ ገልጧል፡፡ አስደናቂ የሆነው የፍጥረት ውስብስብነት፣ ሥርዓት፣ ውበት እና ግዝፈት ስለ እግዚአብሔር ግርማ ሞገስ የሚነግረን ነገር አለ፡፡ ነገር ግን በተለይም በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ስለ ራሱ ነግሮናል፡፡ እግዚአብሔር በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ ራሱን ከገለጠባቸው ልዩ ሁኔታዎች መካከል አንዱ ሥሉስ አሓዳዊነቱ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ሦስቱን የእግዚአብሔር አካላት “ሥላሴ” በማለት ነው የምትጠራው፡፡ በሦስቱ የሥላሴ አካላት በኩል እንዴት ራሱን እንደገለጠ በማጥናት እግዚአብሔርን የበለጠ መረዳት እንችላለን፡፡
ዘዳግም 6፡4 “አምላካችን እግዚአብሔር አንድ እግዚአብሔር ነው” በማለት ያውጃል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ አንድ እግዚአብሔር ብቻ መኖሩን በግልፅ ይናገራል፡፡ ነገር ግን በባሕርይ አንድ በሆኑና ዘላለማዊ እንዲሁም እኩል በሆኑ ሦስት አካላት ይኖራል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ ሦስቱን አካላት አብ፣ ወልድ፣ መንፈስ ቅዱስ በማለት እኩል ያስቀምጣቸዋል (ማቴ. 28፡19፣ 1ጴጥ. 1፡2፣ 1ቆሮ. 12፡4-6፣ 2ቆሮ. 13፡14)፡፡
ሥላሴ ለኛ ታላቅ ምስጢር ነው፡፡ ይህንን በትክክል ሊገልፅ የሚችል ምንም ዓይነት ምሳሌ ስለሌለን እግዚአብሔር አንድ ሆኖ በሦስት አካላት እንዴት እንደሚኖር ሙሉ በሙሉ መረዳት አንችልም፡፡ ውሱን ከሆነው ከኛ ዕይታ ያልተወሰነውን አምላካችንን ሙሉ በሙሉ መረዳት የማይቻል ነው (ኢሳ. 55፡8-9)፡፡ ነገር ግን መጽሐፍ ቅዱስ ይህንን ስለሚያስተምር መተንተንና ማስተማር እንችላለን፡፡ ኤሌክትሪክ መኖሩን ለማመንና ለመጠቀም የግድ የኤሌክትሪክን አሠራር መረዳት እንደማይጠበቅብን ሁሉ ሥላሴንም ሙሉ በሙሉ መረዳት ባንችልም መኖሩ እርግጥ ነው፡፡
ውኃን እንደ ምሳሌ ውሰድ፡፡ አንድ ቁስ ነው (H2O)፡፡ ነገር ግን ፈሳሽ፣ ጋስ (እንፋሎት)ና ጠጣር (በረዶ) ሆኖ በሦስት መልክ ይገኛል፡፡ እግዚአብሔርም አንድ ምንነት (ባህሪ) ያለው አምላክ ሆኖ በሦስት አካላት ተገልጧል፡፡ ነገር ግን ከውኃ በተለየ ሁኔታ የሥላሴ አካላት ሕያው በሆነ መንገድ እርስ በርሳቸው ሕብረት ያደርጋሉ ምክንያቱም አንድ ባህሪ ነውና ያላቸው፡፡

እውነት ለሁሉ

22 Jan, 11:25


ኢየሱስ ስለ ምጽአት ቀን አያውቅምን? በወንድም ናሆም የተዘጋጀ አጠር ያለች አርቲክል በpdf ተጠቀሙባት👌

እውነት ለሁሉ

22 Jan, 10:16


sola scripturaመፅሐፍ ቅዱስ ብቻ ማለት የበላይ እና የመጨረሻው ባለስልጣን መፅሐፍ ቅዱስ ነው። የሚል ህሳቤ ነው የያዘው የሚል ትርጉምና ትምህርት ይሰጣል በፕሮቴስታንት መምህራን ዘንድ እና ክላሲካል ፕሮቴስታንቶችም ይህንኑ ያምናሉ እናም ደስ ይላል አይደል እኛም ይህንን እየተቃወምን አይመስለኝም፣ ምክንያቱም መፅሐፍ ቅዱስ ባለስልጣን ነው ማንኛውም ትምህርት በመፅሐፍ ቅዱስ ስለምንመዝን።

ፕሮቴስታንቶች መጽሐፍቱን ከቤተ ክርስቲያን ትውፊት እንደተቀበሉ ያምናሉ። ታድያ ግን በእነርሱ ሃሳብ የቤተ ክርስቲያን ትውፊት ስህተት ሊሆን ይችላል የሚል ነው። ታድያ ስህተት የማይሆነውን(inffalible) መጽሐፍ ቅዱስ ስህተት ሊሆን በሚችል(Fallible) ትውፊት እንዴት መወሰን ይቻላል? ምናልባት እንደ ክርስቲያኖች ቤተ ክርስቲያንን የእውነት ሁሉ መገኛ ናት ብለው ካላመኑ በስተቀር።?

እውነት ለሁሉ

21 Jan, 19:27


ኢየሱስ ይወዳችኋል

ብዙ ጊዜ ዕቅበተ እምነት ላይ ብቻ ስናተኩር የክርስትናን ዋና መሠረትን እንዘነጋለን። ዕቅበተ እምነት በጣም አስፈላጊ ነገር ቢኾንም እኛ ሰዎች ግን በአመክንዮ የታጠርን ብቻ አይደለንም አንዳንድ ጊዜ ሰው "ክርስትና ለምን እውነት እንደኾነ 10 አሳማኝ ምክንያቶችን" የሚል ሙግት ላይፈልግ ይችላል ይልቅስ የፈለግነውን ተዋስኦ  ብናቀርብ የምንናገረው ነገር ወደ ልቡ ውስጥ ካልገባ ደረቅ እውነት ብቻ ይኾንበታል።

ሐዋርያት ወደ ዓለም ዳርቻ የተላኩት ወንጌልን ሊሰብኩ ነው εὐαγγέλιον - የምስራች ማለት ነው። እግዚአብሔር አንድያ ልጁን አሳልፎ እስኪሰጥ ዓለምን እንዲሁ ወዷል ፤ ወልደ እግዚአብሔር ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስም ኃጢአታችሁን በመስቀል ላይ ተሸክሞ እንዲሁ በጸጋው ድናችኋል እያሉ የምስራቹን መልካም ዜና ወደ ዓለም እየሰበኩ አሰራጩ። በእርግጥ ከእነርሱ ስነ አመክንዮን እየተጠቀሙ የተጠበቀው መሢሕ በእውነትም ኢየሱስ እንደኾነ የክርስትናን እውነታ መጽሐፍ እየጠቀሱ ሞግተዋል ይህም ዐቃቤ እምነት ያደርጋቸዋል። ነገር ግን ዐቃቤ እምነት ብቻ አልነበሩም የምስራቹ ወንጌል ሰባኪያን ናቸው እንጂ።

አሁን ላይ ከኦርቶዶክሳዊያን ወገን ጥሩ የዕቅበተ እምነት ሥራዎች እየተሠሩ ነው በዚህም እንደሰታለን። ነገር ግን ከፕሮቴስታንት አንድ መማር ያለብን ነገር አለ የወንጌል ሥርጭት። ወንጌል ዕቅበተ እምነት ብቻ አይደለም ለተጨነቁት መድኃኒት ላጡት ይኸው መድኃኒት ብሎ መስበክ ነው ፤ ደስታ ለራቃቸው ኹል ጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ እያሉ ማስደሰት ነው ፤ ፍቅር ለራቃቸውም ኢየሱስ ይወዳችኋል ስለ ኃጢአታችሁ ሞቶላችኋል እያሉ ማጽናናት ነው።

በእርግጥም ፍቅር የኾነው ኢየሱስ ይወደናል ስለዚህ በፍቅሩ እንኑር ፍቅሩንም ለኹሉም እናጋራ ፤ ደቀ መዛሙርቱ መኾናችን የሚታወቀው በምናቀርባቸው ሙግቶችና ባለን እውቀት ደረጃ ሳይኾን ከፍቅራችን የተነሣ ነውና!

ኢየሱስ ይወዳችኋል!

ኪዳን ዘኢየሱስ እንደፃፈው

እውነት ለሁሉ

21 Jan, 17:28


ስለ ምልጃ ደስ ሚል ጥላቻ የሌለው ሰውጋ የተደረገ መማማር አንዳድ ጥቅሶችን ባለማወቅ የሚኖሩ ፕሮቴስታንት እንዳሉ ያወኩበት ነው መጀመሪያ ከነበረው መረዳት በኃላ ስለ ምልጃ ኧረ ምርጥ ነው አላለም ተጋበዙ 😁🥰

እውነት ለሁሉ

21 Jan, 16:57


በአንድ ራስ ሁለት ምላስ😁
ጴንጤ ማለት እንደዚ ነው የማያምንበት ነገርኳ ቢሆን ለዛች ሰአት ሰው ፊት ሲል ሌላውን ለመርታት የማያምነውን እንደሚያምን አርጎ ሊያወራ ይችላል እሄ ነገር በአብዛኛው ፕሮቴስታንት ላይ የማየው ነው

እውነት ለሁሉ

19 Jan, 13:44


#በወንጌሉ #ያመናችሁ

በወንጌሉ ያመናችሁ

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ

እውነት ለሁሉ

19 Jan, 07:09


ማቴዎስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።
¹⁴ ዮሐንስ ግን፦ እኔ በአንተ ልጠመቅ ያስፈልገኛል አንተም ወደ እኔ ትመጣለህን? ብሎ ይከለክለው ነበር።
¹⁵ ኢየሱስም መልሶ፦ አሁንስ ፍቀድልኝ፤ እንዲህ ጽድቅን ሁሉ መፈጸም ይገባናልና አለው። ያን ጊዜ ፈቀደለት።
¹⁶ ኢየሱስም ከተጠመቀ በኋላ ወዲያው ከውኃ ወጣ፤ እነሆም፥ ሰማያት ተከፈቱ የእግዚአብሔርም መንፈስ እንደ ርግብ ሲወርድ በእርሱ ላይም ሲመጣ አየ፤
¹⁷ እነሆም፥ ድምፅ ከሰማያት መጥቶ፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው አለ።

እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ

እውነት ለሁሉ

18 Jan, 10:07


“መሠዊያ አለን፥ ከእርሱም ሊበሉ ድንኳኒቱን(ኦሪቱን) የሚያገለግሉ መብት የላቸውም።” ዕብ 13፥10
"መሠዊያውም ቅድስተ ቅዱሳን ይሆናል፤ መሠዊያውንም የሚነካ ሁሉ ቅዱስ ይሆናል።"  ዘጸ 29፥37
“ያን ጊዜ ኢየሱስ በዮሐንስ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መጣ።” ማቴዎስ 3፥13
ጌታ ኢየሱስ በቅዱስ ዮሐንስ እጅ ሊጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ እንደወረደ፤
የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ምልክት የኾነው ታቦተ ሕጉ (መሠዊያው) ከመንበሩ ተነስቶ ወደከተራ(ወደ ታቆረ ውሃ ) ይወርዳል...!!
ተወዳጅ ክርስቲያኖች እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችኹ አደረሰን!

https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!!

እውነት ለሁሉ

18 Jan, 10:02


ቀኑን በሙሉ እንገፋለን የሚረግሙንን እንመርቃለን 😊😊😊❤️

እውነት ለሁሉ

18 Jan, 08:58


መጽሐፍ ቅዱስ
ወደር የማይገኝለት ግሩም መጽሐፍ!
መጽሐፍ ቅዱስ እጅግ የተለየ መጽሐፍ ነው።

በስርጭት ደረጃ ወደር የማይገኝለት የምን ጊዜም ምርጥ መጽሐፍ ነው፡፡

በብዙ ሰዎች በመነበብና በብዙ ቋንቋዎች በመተርጎም ረገድ ወደር የማይገኝለት መጽሐፍ ነው፡፡

የሥነ ቁፋሮና የታሪክ ምሑራን ትክክለኛነቱን ደግመው ደጋግመው አረጋግጠዋል፡፡

አንድ ዕውቅ የሥነ ቁፋሮ ምሑር እንዲህ አለ “የመጽሐፍ ቅዱስን መረጃ የተጻረረ አንድም የሥነ ቁፋሮ ግኝት እንዳልተገኘ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡” 

ያጠኑትና ያመኑት ሰዎች እስከ ዛሬ ከተጻፉት መጻሕፍት መካከል ምርጡ መጽሐፍ መሆኑን ይመሰክሩለታል፡፡

የእግዚአብሔርን የልብ ሐሳብ ለማግኘት የምናነበው ብቸኛው መጽሐፍ ነው፡፡

ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት ሕብረት ሊኖረን እንደሚችልና ከእርሱ ጋር ሕብረታችንን እንዴት ማሳደግ እንደምንችል ይነግረናል፡፡
https://t.me/kettegawa_ewnet

እውነት ለሁሉ

18 Jan, 08:05


መጽሐፍ ቅዱስ የክርስቲያኖች ቅዱስ መጽሐፍ ነው፡፡ በእንግሊዝኛ ባይብል የሚለው “ቢብሊያ” ከሚል የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን “መጻሕፍት” ማለት ነው፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ አንድ መጽሐፍ ብቻ ሳይሆን በተለያዩ ነቢያት፣ በተለያዩ ቦታዎችና በተለያዩ ቋንቋዎች በ1500 ዓመታት ውስጥ የተጻፉ የተለያዩ መጻሕፍት ስብስብ ነው፡፡ የሙሴን ሕግ (ቶራ)፣ የዳዊትን መዝሙር፣ የሰለሞንን መጻሕፍት፣ ኢሳይያስ፣ ኤርምያስ፣ ሕዝቅኤል፣ ዳንኤል፣ ሆሴዕ፣ ኢዩኤል፣ አሞፅ፣ አብድዩ፣ ዮናስ፣ ኢዮብ፣ ሚክያስ፣ ናሆም፣ ዕንባቆም፣ ሶፎንያስ፣ ሐጌ፣ ዘካርያስ፣ ሚልክያስና የመሳሰሉትን ነቢያት መጻሕፍት አካቷል፡፡ በማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስና ዮሐንስ የተጻፈውን የኢየሱስን ወንጌል ይዟል፡፡ የሐዋርያትም ጽሑፎች በውስጡ ይገኛሉ፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ
የሙሴ ሕግ (ቶራ)
የነቢያት መጻሕፍት
መዝሙራት
ወንጌል
‹‹—————- 1500 ዓመታት —————-››
ቁርአን ስለ ተውራትና ወንጌል (ኢንጂል) (3፡3)፣ የነቢያት መጻሕፍት (3፡84)፣ እና መዝሙራት (ዘቡር) (4፡163) ይናገራል፤ ክርስቲያኖችንም “የመጽሐፉ ሰዎች” በማለት ይጠራቸዋል (ቁርአን 5፡68)፡፡
ክርስቲያኖች እነዚህ ሁሉ መጽሐፍት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለምን ኖሯቸው?
ክርስቲያኖች ሁሉንም ነቢያት ስለሚቀበሉና በመካከላቸው አድልዎን ስለማያደርጉ ሁሉም መጽሐፍት በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሏቸው፤ ያነቧቸዋልም፡፡
ሁለተኛ እግዚአብሔር በብዙ ነቢያት በኩል ተናግሮናል፡፡ መጻሕፍታቸው አንዳቸው በሌላቸው ላይ የተገነቡ ሲሆኑ በጋራ እንዲነበቡ የታሰቡ ናቸው፡፡ በጋራ በመሆንም የተሟላውን አምላካዊ መመርያ ይሰጡናል፡፡
ክርስቲያኖች ስለ እግዚአብሔር የሚያምኑት ሁሉ አጠቃላዩን የነቢያት መጽሐፍት ያገናዘበ ነው፡፡
የኢየሱስ ሐዋርያት ወንጌልን የተቀበሉ የነበሩ ቢሆኑም ከሙሴ ሕግ፣ ከነቢያትና ከመዝሙራት እየጠቀሱ ያስተምሩ ነበር፤ መጻሕፍቱንም ያነብቡ ነበር፡፡
ከተለያዩ አገራት የሆኑ ብዙ ሕዝቦች ክርስትናን ሲቀበሉ እንደ ሐዋርያት ሁሉ የሙሴን ሕግ፣ ነቢያትን፣ መዝሙራትንና ወንጌልን ተቀብለው ማንበባቸውን ቀጠሉ፡፡ ዛሬም ቢሆን አንድ ሰው ክርስቲያን ሲሆን ወንጌልን ብቻ ሳይሆን የነቢያትን መጻሕፍት ሁሉ ይማራል፡፡ በክርስቲያን አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሁሉም የነቢያት መጻሕፍት በአደባባይ ይነበባሉ፣ ይሰበካሉ፡፡
ክርስትና ሰዎች የሙሴን ሕግ፣ ነቢያትንና መዝሙራትን ከወንጌል ጋር በማጣመር እንዲያነብቡና እንዲቀበሉ በማስተማር ነው የተስፋፋው፡፡ የነቢያት ሁሉ መጻሕፍት በሰው ልጆች ሁሉ ይታወቁ ዘንድ ክርስቲያኖች እነዚህን መጻሕፍት ወደ አብዛኞቹ ቋንቋዎች ተርጉመዋል፡፡

እውነት ለሁሉ

17 Jan, 06:32


ነገረ ስቅለት

ዛሬ አርብ ምሽት 2:30 ላይ በወንድማችን

አል ዕራድ ቤት 👇

https://www.tiktok.com/@a..l..r..a..e..d?_t=ZS-8t8OZIwoWjH&_r=1

እውነት ለሁሉ

17 Jan, 06:10


የቀጠለ
ለእርኩስ መንፈስ ሙስሊሞች ሲከራከሩ ተመልከቱ ጥቅስን ሚያቀብሏቸው ኡስታዞች ናቸው እሄ ማለት ኡስታዞቹም የእርኩስ መንፈስ ወዳጆች መሆናቸውን ያሳያል

ተመልከቱ ሰይጣን እንዳያስተውሉ እንዳጨለመባቸው ማር 9:25 ክርስቶስ ተሳደበ ብሎ ነው የጠቀሰው ደንቆሮ ዲዳ ያለው ርኩስ መንፈስን ነው👈 ማር9:25 እና ልጁ ለእርኩስ መንፈስ እየተከራከረለት ነው ምክንያቱም አላህ ርኩስ መንፈስ ስለሆነ

ማርቆስ 9
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ከሕዝቡ አንዱ መልሶ፦ መምህር ሆይ፥ ዲዳ መንፈስ ያደረበትን ልጄን ወደ አንተ አምጥቼአለሁ
>>ከመጀመሪያውኑ መንፈሱ ዲዳ መንፈስ ነው ዲዳ መባሉ መገለጫው ነው

ሰይጣን ሚባል ስም ለልጆቻን ስም አናወጣም ቃሉን ለጥሩ ነገርም አናውልም
ሰይጣንን ሰይጣን ብለን ለምን እንሰይመዋለን ስድብን መጥፎ ነገርን? ስለዚህ በሙስሊሞች እምነት መሠረት ሰይጣንን ሰይጣን ስንል እየሰደብነው ነው ሊባል ነው ስለዚህ ቅዱስ የተባረከ ወዘተ ማለት አለብን ሊባል ነው እንደ ሙስሊሞች እምነት

ሲጠቃለል በፎቶው ላይ ምታዩት ማሰቢያ እያላቸው አለማሰብን ማየት እቻሉ አለማየትን መስማት እየቻሉ አለመስማትን እውርነትና ድንቁርናን የመረጠ መሆኑን ወይም ልክ ነኝ ካለ በጽሁፉ ላይ እንዳለው ለእርኩስ መንፈስ እንዴት እንደሚከራከሩ የእርኩስ መንፈስ ወዳጅነታቸውን ምናይበት ነው። ጥቅሱን ሰጪዎቹ ኡስታዞቹም ስለሆኑ
ኢየሱስም ሕዝቡ እንደ ገና ሲራወጥ አይቶ ርኵሱን መንፈስ ገሠጸና
— ማርቆስ 9፥25

ጌታ ክርስቶስ ርኩስ መንፈስን የገሰጸበት አንቀጽ ተሰጥቷቸው ለእርኩስ መንፈስ እንደሚከራከሩ የርኩስ መንፈስ ተቆርቋሪ መሆናቸው ያላወቃችሁ እወቁ ከዚ በኃላ

እውነት ለሁሉ

16 Jan, 16:48


“እናንት ደንቆሮዎች፥ የውጭውን የፈጠረ የውስጡን ደግሞ አልፈጠረምን?”
  — ሉቃስ 11፥40

አንዳድ ሰዎች እቺን ጥቅስና ተመሳሳዮችን በመያዝ ስድብ በማለት ራሳቸው ለፈጠሩት ይቀለኛል ብለው ለሚያመልኩት የራሳቸውን አስተሳሰብ ያጽናናቸው ዘንድ ለማብጠልጠል ይጠቅሷታል

ፈገግ ሚያስብለው 😁
እሄን ጥቅስ ለትችት ይጠቅሱታል
“እናንት ደንቆሮዎች፥ የውጭውን የፈጠረ የውስጡን ደግሞ አልፈጠረምን?”

  — ሉቃስ 11፥40

እሄን ግን አይጠቅሱትም👇
ስለዚህ እያዩ ስለማያዩ እየሰሙም ስለማይሰሙ ስለማያስተውሉም በምሳሌ እነግራቸዋለሁ።”
  — ማቴዎስ 13፥13

ግን ምን ልዩነት አለው ? ምንም ልዩነት የለውም ሁለቱም ጥቅስጋ የተጠቀሱት ጆሮና አይን ያላቸው ናቸው። እንደዚ ከሆነ

ሉቃ10:11 እንደሚጠቅሱት እያዩ የማያዩ እየሰሙ የማይሰሙ ሚለውን አይነኳትም ለምን የሙስሊሞች ግብርቸው ነው እውነት እንደሆነ እያወቁ እየተረዱ ላለመረዳት ላለማወቅ ሚጥሩ ስለሆኑና እነሱን ገላጭ ቃሉም ክርክር የማያስነሳ ስለሆነ ነው።
ግን ለማብጠልጠል የማያነሱት ማቴ13:13ን እየሰሙ የማይሰሙ ማለት ምንም ማለት ነው ?ጆሮ አለህ ግን አትሰማም ደንቁረሀል ማለት ነው እንደዚሁ ሲባል ግን ስድብ እንዳልሆነ ሚታወቀው
እሄን👇
ስለዚህ እያዩ ስለማያዩ እየሰሙም ስለማይሰሙ ስለማያስተውሉም በምሳሌ እነግራቸዋለሁ።”
  — ማቴዎስ 13፥13
ለማብጠልጠሊያነት ስለማያነሱ ነው ስለዚህ ወደ ደንቆሮ ሚለውን ስንገባ እንደስድብ አርገው ሊያነሱት አይገባም ነው ሊያነሱት ሚያስችላቸው አደለም ካለማወቅ ሚያረጉት ነው በሌላም context ተከትለን ማየት አለብን መንስኤ ሚለውን

አንድ ምሳሌ ላሳያችሁ በትምህርትም ያየነው ስለሆነ (world health organization) WHO አንድ ሰው ጤናማ ሚባለው mental physical social ደህንነት ያለው እነዚን ሲሆን ነው ይላላ ከጠቀሳቸው ላይ social እናንሳና ማህበረሰባዊ ነገራቶች ላይ ተግባቦት የሌለው ሰው በሽተኛ ነው እያለ ነው? ለምን whoን ሰደብከን ብላችሁ መግለጫ አልሰጣችሁም እንደ አጠቃለይ ሰዎችን ስለሆነ የተናገረው እና ይሄን ያየነው ምን ማለት ነው ሙስሊሞች ለአእምሮአቸው ምቹ አርገው ላደላደሉት አላህ ላይ ለሚነሳባቸው ማጽናኛ ብቻ እንጂ እንደምትሉት ስድብ አደለም

ጳውሎስም እንዲ ይላል
ሮሜ 1
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰-²¹ የማይታየው ባሕርይ እርሱም የዘላለም ኃይሉ ደግሞም አምላክነቱ ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ ከተሠሩት ታውቆ ግልጥ ሆኖ ይታያልና፤ ስለዚህም እግዚአብሔርን እያወቁ እንደ እግዚአብሔርነቱ መጠን ስላላከበሩትና ስላላመሰገኑት የሚያመካኙት አጡ፤ ነገር ግን በአሳባቸው ከንቱ ሆኑ የማያስተውለውም ልባቸው ጨለመ።
²² ጥበበኞች ነን ሲሉ ደንቆሮ ሆኑ፥

ጳውሎስ እያነሳው ያለው ጆሮና አይን ስለሌላቸው ሰዎች ሳይሆን አይንና ጆሮ ስላላቸው ነው ግን እሄ ማለት ስድብ ማለት አደለም እየሰማህ እንዳልሰማ እያወቁ እንደማያቁ ለእግዚአብሔር ክብር  ያጥላሉ አለማወቅን እያወቁ አልመሳማትን አለማወቅን የመረጡ በነሱ የተጠበቡ ሚመስላቸው ግን የተሰጠቻውን ጸጋ ያልተጠቀሙበት የማይሰሙ ማለት ነው

ሲጠቃለል
ደንቆሮ ሚባለው ቃል ስድብ አደለም ደንቆሮ ሚለውን ቃልም በሌላ ቦታ ራሱ ጌታችን ኢየሱስ ፍቹን ምን ማለት እንደሆነም ማቴ 13:13 ላይ እየሰሙ ማይሰሙ ማስተዋል እየቻሉ ማያስተውሉ የግብራቸው ስም ነው እሄ ማለትም የሚሰርቅ ሰው ስለ ሰረቀ በስራው ግብሩ ምክንያት ሌባ ተብሎ ስም ይሰጠዋል እንጂ ጎበዝ አይባልም ልክ እንደዚሁ ስድብ ማለት ሳይሆን የግብር ስም ነው

እነሱ ባመጡት ሀሳብ መሠረትና ስድብ ሚለውን ይዘው ስለተረጎሙ በምንም አይነት ቢሆን ቃሉን የሚሉት ወይም የተጠቀመው ተሳዳቢ ወይም ስድብ ነው በማለት ሙስሊሞች ስለሚያነሱት በቁርአኑም አላህ ደንቆሮ ብሎ የተናገረበትን በማውጣት በእነሱ መረዳት መሠረት አላህ ተሳዳቢ ነው ማስረጃውም

وَمَثَلُ الَّذِينَ كَفَرُوا كَمَثَلِ الَّذِي يَنْعِقُ بِمَا لَا يَسْمَعُ إِلَّا دُعَاءً وَنِدَاءً ۚ صُمٌّ بُكْمٌ عُمْيٌ فَهُمْ لَا يَعْقِلُونَ

የነዚያም የካዱት (እና ወደ ቅን መንገድ የሚጠራቸው ሰው) ምሳሌ እንደዚያ ድምጽንና ጥሪን በስተቀር ሌላን በማይሰማ (እንስሳ) ላይ እንደሚጮህ ብጤ ነው፡፡ (እነርሱ) ደንቆሮዎችዲዳዎች፣ ዕውሮች ናቸው፤ ስለዚህ እነርሱ አያውቁም፡፡ የላሚቷ ምዕራፍ ቁጥር 171 ላይ

እንደውም ብዙ አይነት አርጎ በይበልጥ ነው የተናገረው ደንቆሮዎች ዲዳውች ዕውሮች ስላለ አላህ ተሳዳቢነው

እዛው የላሚቷ ምዕራፍ ቁጥር 18ላይም

صُمٌّ بُكْمٌ عُمْيٌ فَهُمْ لَا يَرْجِعُونَ

(እነሱ) ደንቆሮዎች፣ ዲዳዎች፣ ዕውሮች ናቸው፤ ስለዚህ እነርሱ አይመለሱም፡፡

በማለት አላህ ይሰዳባል ብዙ መዘርዘር ይቻላል እኛ እናንተን ማሸማቀቅና ማሳደድ ስላልሆነ ነው። ስለዚህ አላህ ተሳዳቢ ነው ።

ማንኛውም ሙስሊም ጥላቻ ከሌለው ለመስማትና ለመረዳት ሚፈልግ የተረዳውም በቅን ልቦና እውነተኛውን ለመምረጥ የሚጥር ከሆነ ሙስሊም አይሆንም ሙስሊም ሚሆንበት ምንም ምክንያት አይኖርም

“ጠቢብ እነዚህን ከመስማት ጥበብን ይጨምራል፥ አስተዋይም መልካም ምክርን ገንዘቡ ያደርጋል።”
  — ምሳሌ 1፥5

እውነት ለሁሉ

15 Jan, 22:39


በአጭበርባሪዎቹ አስታዞች ላይ እንደዚ አይነት ሀቀኛ ሙስሊምም አለ ጥቂት ቢሆንም 😊
እስልምናን በብር የሚያሳምኑ እንደሆኑ ሀቁን ሚያምን አንዳዶች ሙስሊም እንዳሉ ይጠቅማችኃል ተማሩበት ባለማመን ራሳችሁን አታታሉ

እውነት ለሁሉ

15 Jan, 21:31


ሰማይ እንደ ውሀ ታፈሰ አለም አቀፍ ቤተክርስቲያን ሚባል መጣ 🙈😂😂

እውነት ለሁሉ

14 Jan, 20:34


ያው ከኡስታዛችሁ 😁
ይሄኔ እኛ ብንሆን የጠቀስነው ስንት ትላችሁን ነበር በቃ ልታጣብቁን ነው 🤔

እውነት ለሁሉ

13 Jan, 16:45


“ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።” ሉቃስ 2፥21
እንኳን አደረሳችኹ ተወዳጆች...🥰
ኢየሱስ የሚለው ስሙ መዳኛ ነው 🥰
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

እውነት ለሁሉ

12 Jan, 20:52


ከጠቀማችሁ😁✌️

እውነት ለሁሉ

12 Jan, 06:13


ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት፡፡
ክርስቶስ በቅዱስ ደሙ መሥርቷታል፤ አንጽቷታል፤ ቀድሷታልና ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ናት ኤፌሶን 5 ፥ 26፡፡የቤተ ክርስቲያን ቅድስና የተገኘው ቅድስና የባሕርይ ገንዘቡ ከሆነው ከጌታችንና ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ በመሆኑ ወደ እርስዋ የገቡ ርኩሳን ይቀደሳሉ እንጂ በውስጥዋ ያሉ ሰዎች በኃጢአት በክህደት ቢረክሱ እርስዋ አትረክስም፡፡ ዳሩ ግን እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ ባለው መሠረት በእርሱ ያመኑ በቤተ ክርስቲያን ጥላ ሥር የተጠለሉ ሁሉ ቅድስናን ገንዘብ ሊያደርጉ ይገባል፡፡ቤተክርስቲያን ቅድስት (የተለየች) ናት ስንል ስለ አራት ነገሮችን ያመለክታል፡፡

አንደኛ፡ በደሙ የመሠረታት ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ነውና ቤተክርስቲያን ቅድስት ናት፡፡ 1ጴጥ 1፡15-16 ሐዋ 23፡20 ቤተክርስቲያን የክርስቶስ አካሉ ናትና ቅድስት ናት፡፡ እርሱም መሠረቷ አካሏና ጉልላቷ ስለሆነ ቅድስት ናት፡፡

ሁለተኛ፡-ቤተክርስቲያን የቅድስና ሥራ (አገልግሎት) የሚፈጸምባት የጸሎት ቤት ናትና ቅድስት (የተለየች) ናት፡፡ የተለየችው ለቅድስና ሥራ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ በቅድስት ቤተክርስቲያን የቅድስና ያልሆነ ሥራ መሥራት አይገባም፡፡

ሦስተኛ፡- ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ያመኑ የሰው ልጆች ምሥጢራትን ተካፍለው (ተጠምቀው ንስሐ ገብተው ሥጋና ደሙን ተቀብለው) ቅድስና ያገኙባታልና ቅድስት ናት፡፡ የቅድስና መገኛ ስፍራ ናትና ቅድስት ናት፡፡

አራተኛ፡- ቤተክርስቲያን ቅድስት የሆነችው የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ ናትና ቅድስት ናት፡፡ ወደ ሰማያዊት መንግስት የምታደርስ በምድር ላይ ያለች የክርስቲያኖች ቤት ናትና ቅድስት ናት፡፡ በምድር ላይ ለእግዚአብሔር የተለየች ቅድስት ናት፡፡

አንዳንድ ወገኖች ብዙ ኃጢአት የሚሠሩና በደልን የሚፈፅሙ ሰዎች በቤተክርስቲያን ስላሉ ቤተክርስቲያን የምትረክስ (ቅድስናዋ የሚቀንስ) ይመስላቸዋል፡፡ እውነታው ግን እነዚህ ሰዎች በጊዜው በንስሐ ካልተለመሱ ራሳቸው ይረክሳሉ እንጂ ቤተክርስቲያን አትረክስም፡፡ የቤተክርስቲያን ቅድስናዋ ዘላለማዊና የማይለወጥ ስለሆነ አትረክስም፡፡ ሰው ቢያከብራት ራሱ ይከብራል፡፡ ባያከብራት ደግሞ ራሱ ይረክሳል፡፡ ይህም በአፍኒንና በፊንሐስ እንዲሁም በሐናና በሳጲራ እንደሆነው ነው፡፡ ሐዋ 5፡1 1ኛ ሳሙ 2፡12 ለምሳሌ በቆሻሻ ላይ የፀሐይ ብርሀን ቢወጣበት ቆሻሻው ይሸታል እንጂ የፀሐይ ብርሀኑ ምንም አይሆንም፡፡ የቤተክርስቲያን ቅድስናም ልክ እንደ ፀሐይ ብርሀን ነው፡፡

ወሰላሙ አለይኩም✌️

እውነት ለሁሉ

11 Jan, 08:50


ቤተክርስቲያን ዘላለማዊትና የማትታደስ ናት፡፡
ዘላለማዊነት አንዱ የቤተክርስቲያን መገለጫ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን ዘላለማዊት ናት፡፡ መሠረቷ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘላለማዊ ነውና እርሷም ዘላለማዊት ናት፡፡ በአካለ ሥጋ ያሉ ክርስቲያኖችና በአካለ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን ከክርስቶስ ጋር ያላቸው አንድነት ዘላለማዊ ነውና ቤተክርስቲያንም ዘላለማዊት ናት፡፡ ዘላለማዊ ናት ስንል ዘላለማዊነቷ በመጠበቅ (ጠብቆ ይነበብ) እንጂ በመታደስ (እየታደሰች) አይደለም፡፡ ክርስቶስ የምታረጅ፣ የምትለወጥ ወይም የምትጠፋ ቤተክርስቲያን አልመሠረተም፡፡ የማያረጅ ነገር ደግሞ አይታደስም፡፡ ሁል ገዜ አዲስ ነውና፡፡ ከዚህ ውጭ ቤተክርስቲያን ትታደስ ማለት ግን የሚከተሉትን መሠረታዊ ስህተቶች/ክህደቶች ያስከትላል፡፡

1.ቤተክርስቲያን ትታደስ ማለት፡- ሐዋርያዊ መሠረት አያስፈልጋትም በየጊዜው ሌላ መሠረት ያስፈልጋታል ማለት ነው፡፡

2.ቤተክርስቲያን ትታደስ ማለት፡- መሥራቿ አጉድሎ ነው የመሠረታት ናትና እኛ እናሟላት እንደማለት ነው፡፡

3.ቤተክርስቲያን ትታደስ ማለት፡- በእርሷ የነበሩ በእርሷ የኖሩ አልፀደቁም እንደማለትም ነው፡፡

4.ቤተክርስቲያን ትታደስ ማለት፡- የምትፈጽማቸው ምሥጢራት ለድኅነት አያበቁምና ይሻሻሉ ማለት ነው፡፡

5.ቤተክርስቲያን ትታደስ ማለት፡- እኛ ከቀደሙት የተሻልን ነንና የተሻለች ቤተክርስቲያን እንመሥርት እንደማለት ነው፡፡

ስለዚህ ቤተክርስቲያን ትታደስ የሚለው አስተሳሰብ መሠረታዊ ስህተት ነው፡፡ አምስቱ አዕማደ ምሥጢራት የሚቀየሩ ወይም የሚሻሻሉ አይደሉም፡፡ ጸንተው የሚኖሩ እንጂ፡፡ ነገር ግን ሁለት በቤተክርስቲያን ዘንድ እድሳት የሚያስልጋቸው ነገሮች አሉ፡፡ እነርሱም የቤተክርስቲያን አስተዳደርና የክርስቲያኖች ሕይወት ናቸው፡፡ እነዚህ ሁለቱ ከቤተክርስቲያን አስተምህሮ አንጻር በየጊዜው እየታዩ ሊሻሻሉ ይችላሉ፡፡ አስተዳደሩን ማዘመን ያስፈልጋል፡፡  የምዕመናን ሕይወት ደግሞ በንስሐ እየታደሰ ይኖራል፡፡ ከዚህ ውጭ ግን ሰውን የምታድሰው ቤተክርስቲያን እራሷ አትታደስም፡፡

ወሰላሙ አለይኩም✌️

እውነት ለሁሉ

10 Jan, 16:37


ጉድ ስሙ ኡስታዞች ሚዲያውን ለመቆጣጠርም ብለው ድራማ ምን አይነት የወረደ ተግባር እንደሚያረጉ
.
.
.
.
ክርስቲያኖች ቀየርን ክርስቲያን አረግን ሚሉት አስተምረው አሳውቀው ነው ኡስታዞች እንደ ክርስቲያኖች ማረግ ስለማይችሉ የወረደ ተግባር ማጭበርበር ሚሰሩት
ለዚ ነው ሙስሞች ኢስላም ሆኑ ብለው በቲክቶኩ ሚያናፍሱትን ውሸት ብለን ማናምናችሁ እስከ ዛሬ ያላመናችሁ ከዚ ሰአት በኃላ እነሆ እምኑ

እውነት ለሁሉ

07 Dec, 10:18


የቀጠለ


የቤተክርስቲያን ዓላማዋ አንድ ነው፡፡
የአሐቲ ቤተክርስቲያን ዓላማዋ አንድ ብቻ ነው፡፡ እርሱም ለሰው ልጅ ሁሉ ቅዱስ ወንጌልን በማዳረስ ሰው ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አምኖ፣ በስሙም ተጠምቆ፣ ምግባር ትሩፋትን ሠርቶ የእግዚአብሔርን መንግስት እንዲወርስ ማድረግ ነው፡፡ ከዚህ የተለየ ዓላማ ያላት ቤተክርስቲያን የለችም፡፡ ከዚህ የተለየ ምድራዊ ዓላማ ይዘው በቤተክርስቲያን ስም የሚጠሩ ስብስቦች ሐሰተኛ እንጂ እውተኛ፣ ምድራዊ እንጂ ሰማያዊ ቤተክርስቲያን ሊባሉ አይችሉም፡፡ እውነተኛይቱ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ተቋም ስለሆነች ዓላማዋም ሰማያዊ እንጂ ምድራዊ አይደለም፡፡ ምንም እንኳን አንዳንድ ምድራዊ ዓላማ ያላቸው ‘አገልጋዮች’ በቤተክርስቲያን ቢኖሩም የቤተክርስቲያንን ዓላማ ግን ምድራዊ አያደርጉትም፡፡  በምድር ያለችው ቤተክርስቲያን ምሳሌ የሆነቻት ሰማያዊት ኢየሩሳሌምም አንዲት ናት፡፡ በምድር ባለችው አንዲት ቤተክርስቲያን የጸኑት ክርስቲያኖች እንደሚሰበሰቡ ሁሉ ነጻ በምታወጣ በኢየሩሳሌም ሰማያዊትም የጸደቁት፣ በጌታ ቀኝ የሚቆሙት ይሰበሰባሉ፡፡

ቤተክስቲያን የአንድነት ጉባዔ ናት፡፡
ቤተክርስቲያን በምድር ያሉ ክርስቲያኖች፣ በሰማይ በአፀደ ነፍስ ያሉ ቅዱሳን፣ እንዲሁም ቅዱሳን መላእክት በአንድነት ለምስጋና የሚተጉባት የሰማይ ደጅ ናት (ዘፍጥረት 28፡17)፡፡ እነዚህ ሁሉ ቅዱሳን ከእግዚአብሔር ጋር ያላቸው አንድነት (ውህደት) ነው ቤተክርስቲያን የሚባለው፡፡ በዚህም መሠረት ቤተክርስቲያን ሁሉም ሰውና መላእክት በአንድነት የሚያመሰግኑባት እንጂ ሰው በየወገኑ እየተከፋፈለ የሚወነጃጀልባት አውድ አይደለችም፡፡ አንድነትን በአደባባይ ለይምሰል እየሰበኩ በተግባር ግን ልዩነትን የሚያስፋፉ ወገኖችም በንስሐ እስካልተመለሱ ድረስ ከቤተክርስቲያን ወገን አይደሉም፡፡ ራሳቸውን ቤተክርስቲያን (የክርስቶስ ቤተመቅደስ) ሳያደርጉ በሕንጻ ቤተክርስቲያን አካባቢ ስለተመላለሱ ብቻ የቤተክርስቲያን አካል አይሆኑም፡፡ እውተነኞቹ ክርስቲያኖች በቤተክርስቲያን ያላቸው አንድነት በፍቅር የተገነባ የመንፈስ አንድነት ስለሆነ አንዱ ለሌላው ስለመልካም ነገር የሚጸልይበት አንድነት ነው፡፡ እዚህ ላይ ማስተዋል የሚያስፈልገን ቤተክርስቲያን የአንድነት ጉባዔ ናት ሲባል የአምልኮ፣ የፍቅር፣ የሰላም፣ የመተሳሰብ፣ የመተባበር፣ የመደጋገፍ ጉባዔ ናት ማለት ነው፡፡

እውነት ለሁሉ

07 Dec, 10:15


ስለእኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው

ኢየሱስ ክርስቶስ ስለእኛ ይማልዳል ስንል የክርስቶስ ምልጃ አንድ ጊዜ ቀርቦ ለኹልጊዜ ይሠራል ማለታችን ነው። ቅዳሴ አትናቴዎስ ቁጥር 144 ላይ " ወልድ ሆይ እንደ ታመመ ሰው አሰምተህ ተናገር ኤልማስ ላማ ሰበቅታኒ በል። በአፋቸውም ውስጥ እያለ አባ አባቴ ሆይ ሥጋዬን የበሉትን ደሜን የጠጡትን ማራቸውም ይቅር በላቸው በል" እያለ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ በታላቅ መቃተት ያቀረበው ምልጃ ዛሬም በሥጋውና ደሙ ገና በአፋችን ሳለ እንደሚሠራልን ያስገነዝበናል። የክርስቶስ ምልጃ ፍጹም ነው እንደ ብሉይ ኪዳን ሊቃነ ካህናት በየዓመቱ መደጋገም አይጠበቅበትም አንድ ጊዜ ባቀረበው ምልጃ ዘለዓለም ሊያድነን ይችላል "ስለ እነርሱም ሊማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራል" እንዲል ቅዱስ ጳውሎስ።

እንዲህ ያለ ከፍ ያለ የታመነ ሊቀ ካህናት በሰማይ አለን ለኃጢአታችን ሥርየት አንድ ጊዜ ባፈሰሰው ደም ዛሬም ይምረናል "ሊቀ ካህናት ዘይቀውም ሎሙ ለቅዱሳን በደብተራ ስምእ እንተ እግዚአብሔር ተከላ ወእቲ ኢየሱስ ክርስቶስ-እግዚአብሔር በተከላት ምሥክር ድንኳን ውስጥ ለቅዱሳን የሚቆምላቸው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" እንዲል አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ። አንድ ጊዜ ወደ ቅድስተ ቅዱሳን በደሙ ገብቷል እኛም የክርስቶስን ደም አንድ ጊዜ በማቅረብ ተቀድሰናል እስከ ሕይወት ፍጻሜያችንም እንቀደሳለን ምልጃው ድግግሞሽ የማይስፈልገው አንድ ጊዜ ለዘለዓለም የቀረበ ፍጹም ነውና!

በአብ ዘንድ የታመነ ጠበቃ አለን ለኃጢአታችን ብቻ ሳይኾን ለዓለም ኹሉ ኃጢአት ሥርየት አንድ ጊዜ የቀረበ አስታራቂ በአብ ቀኝ አለን ልያውም በድካማችን የሚያግዘን ፈተናችንን ኹሉ የተፈተነ ሊራራልን የሚችል ሊቀ ካህናት በሥራው ኹሉ የታመነ ነው ወደ እርሱ እንቅረብ ከኃጢአታችን ኹሉ በቅዱስ ደሙ ያነጻናልና!

እውነት ለሁሉ

06 Dec, 20:42


ከኩረጃው ባሻገር ወሳኝ ነጥብ ማንሳት እችላለን
ቁርአኑ ለኢየሱስ የተነገረበትን ለአላህ አምላክ ለሚባለው መስጠቱ ለራሱ ለኢየሱስ የተነገረበት አንቀጽ አምላክነቱን እንደሚገልጽ አላህ ማወቁን  ነው ሚያስረዳው

አመክንዮ ነጥብ ማንሳት ያስችላል እሱም ምድነው

በቁርአኑ ላይ የሰዎች የሕይወታቸውን ወይም ሞታቸውን ለፈጣሪ እንደሆነ ለፈጣሪ ለአላህ ሚሰጥ ተግባር እንደሆነ እናያለን ከቁርአኑ

ከተኮረጀበት ዋናው መጽሐፍ ቅዱስም መሞታችን ሕይወታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ይገልጻል ። ልክ እንደቁርአኑ ማለት

በዚ ላይ ተነስተን የኢየሱስን አምላክነት መናገር ያስችላል በሕይወት መኖር መሞትም ለአላህ ፈጣሪ ለሚሉት የሚውል ነው ካለን ቁርአኑ

ተመሳሳዩን እንደ ቁርአኑ መጽሐፍ ቅዱስም ስለሚናገር ኢየሱስ አምላክ ነው ።

እውነት ለሁሉ

06 Dec, 19:48


ሰበር ዜና ተዘርፈናል ወገን ለኢየሱስ የተነገረበትን ሀሳብ ወስዶ ለአላህ ተብሎለት እናገኛለን 👇

ለእኔ ሕይወት ክርስቶስ፥ ሞትም ጥቅም ነውና።”
  — ፊልጵስዩስ 1፥21

قُلْ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحْيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ

«ስግደቴ፣ መገዛቴም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለአላህ ነው» በል፡፡ 6፥162

እውነት ለሁሉ

06 Dec, 11:40


አንዲት ቤተክርስቲያን (በቃልና በተግባር)

አርዮስን ለማውገዝ በጉባዔ ኒቅያ የተሰበሰቡ ቅዱሳን አባቶች (ሠለስቱ ምዕት) ‹‹ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንተ ላዕለ ኩሉ ጉባዔ ዘሐዋርያት/ከሁሉ በላይ በምትሆን የሐዋርያት ጉባዔ በአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እናምናለን›› በማለት ቤተክርስቲያን አንዲት (አሐቲ) መሆንዋን ደንግገዋል፡፡ ለቤተክርስቲያናችንም ይህ የቤተክርስቲያን አንድነትን የሚያስረግጠውን ድንጋጌ የሃይማኖት ጸሎት (ጸሎተ ሃይማኖት) ዋና መመሪያዋ ነው፡፡ ቅድስት ቤተክርስተያን በቅዳሴዋም ‹‹ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተክርስቲያን አሐቲ ቅድስት ጉባዔ እንተ ሐዋርያት ርትዕት በኀበ እግዚአብሔር/በእግዚአብሔር ፊት የጸናች ስለምትሆን የሐዋርያት ጉባዔ አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን ጸልዩ›› እያለች ታውጃለች፡፡ በእነዚህና መሰል ጸሎቶች የቤተክርስቲያንን አንድ (አሐቲ) መሆን ስትመሰክር ትኖራለች፡፡ በዚህ የአስተምህሮ ጦማር ቤተክርስቲያን አንዲት ናት ሲባል የአንድነቷ መሠረትና መገለጫዎች ምን እንደሆኑ በአጭሩ እናቀርባለን፡፡

ቤተክርስቲያን መሪዋ አንድ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
የቤተክርስቲያን መሪዋ አንድ ነው፡፡ እርሱም መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ የቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስም ተጠሪነቱ ለአንዱ መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡ በአንዱ መንፈስ ቅዱስ የምትመራ አንዲት ቤተክርስተያን እንጂ ከአንድ በላይ ቤተክርስቲያን የለችም፡፡ ያችውም ከቅዱሳን ሐዋርያት የተማረችውን ትምህርተ ሃይማኖትና ሥርዓተ ቤተክርስቲያን ከሐሰት ትምህርትና ከመናፍቃን ቅሰጣ በመለየት በምድር ያለች የሰማያዊት ኢየሩሳሌም አምሳል የሆነች የክርስቶስ ቤተክርስቲያን፣ በቀጥተኛነቷና ክህደት ባለመቀላቀሏ ኦርቶዶክሳዊት የምትባል፣ በጌታችን ፍጹም አምላክነትና ፍጹም ሰውነት ተዋህዶ በማመኗ ደግሞ ተዋህዶ የምትባል ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ናት፡፡ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመሠረተልን አንዲት ቤተክርስቲያንን ነው፡፡ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ቤተክርስቲያን አልመሠረተም፡፡ እንድንመሠረትም አላስተማረንም፡፡ ከዘመናት በኋላ ቤተክርስቲያን ተከፋፍላ እውነት ያልተዋጠላቸው ወገኖች ራሳቸውን እየለዪ የራሳቸውን ‘ቤተክርስቲያን’ በየዘመናቱ ቢመሠርቱም እውነተኛዋ ቤተክርስቲያን ግን አንዲት ናት፡፡ ስትመሠረትም፣ ከተመሠረተችም በኋላ፣ ዛሬም፣ እስከዓለም ፍጻሜም አንዲት ሆና ትኖራለች፡፡ በየዘመናቱ የሚነሱ ደገኛ አገልጋዮችም በመንፈስ ቅዱስ የተገለጠላቸውን እውነት እየመሰከሩ በዚች አሐቲ ቤተክርስቲያንም በመንፈስ ቅዱስ የሚከናወኑትን ምስጢራት ተካፍይ በመሆን በክርስትናቸው ጸንተው ለክብር ይበቃሉ፡፡

የቤተክርስቲያን  ራሷ እና መሠረቷ አንዱ ክርስቶስ ነው፡፡
ክርስቶስ የቤተክርስቲያን ራስ ነው፡፡ እርሱ የቤተክርስቲያን መሠረትም ነው (ማቴ 16፡16)፡፡ በክቡር ደሙ የዋጃትም እርሱ ነው፡፡ ቤተክርስቲያን እግዚአብሔር ወልድ ሰው በመሆኑ ከሰው ባህርይ ጋር በተዋሕዶ አንድ ሆኖ የመሠረታት ናት፡፡ ክርስቶስ ትናንት ዛሬና ነገ እስከ ዘለዓለም ድረሰ ያው ነውና የመሠረታት ቤተክርስቲያንም አንዲት ሆና ትኖራለች፡፡ ”እኔ የወይን ግንድ ነኝ፣ እናንተም ቅርጫፎች ናችሁ’ እንዳለው ሁላችን በአንዱ ግንድ በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የተመሠረትን ቅርጫፎች ነን፡፡ ቤተክርስቲያንም በዚህ አንድ ግንድ ላይ የተመሠረቱ ክርስቲያኖች ኅብረት ስለሆነች አንዲት ናት፡፡ በአንድ ግንድ ላይ የተመሠረትን ልንለያይና ልንከፋፈል አይገባም፡፡ ‹‹ከተመሠረተው በቀር ማንም ሌላ መሠረት ሊመሠርት አይችልምና፥ እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው (1ኛ ቆሮ 3 : 11)›› እንደተባለው አሐቲ ቤተክርስቲያን በዚህ መሠረት ላይ የተመሠረተች ስለሆነች ሌላ አዲስ መሠረት ወይም እንደ አዲስ መመሥረት አያስፈልጋትም፡፡ አንዳንዶች ባለማወቅ አንድ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ሲተክሉ ራሳቸውን ‹‹መሥራች›› ብለው ይጠራሉ፡፡ ይህ አባባል ከምድራዊ ሕግ አሰራር የተቀዳ፣ በአብዛኛውም ቤተክርስቲያንን ለግል ጥቅምና ዝና መጠቀሚያነት የሚያስቡ የብኩን ትውልድ አካላት የሚጠቀሙበት ነው፡፡ የአሐቲ ቤተክርስቲያን መሥራች ራሱ ክርስቶስ ስለሆነ ይህ አባባል ለስሕተት ይዳርጋል፡፡

       (ይቀጥላል)

እውነት ለሁሉ

06 Dec, 11:32


ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስለምስጢረ ቁርባን የምታምነው እምነት ከሌሎች የሚለየው እንዴት ነው?
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ስለምስጢረ ቁርባን የምታምነው እምነት አማናዊ ለውጥ (Definitive change) ሲሆን ይህም ‹ፍጹም በሆነ አምላካዊ ምስጢር ኅብስቱ ተለውጦ አማናዊ የክርስቶስ ሥጋ፣ ጽዋውም ተለውጦ አማናዊ የክርስቶስ ደም ይሆናል›› የሚል ነው፡፡ ይህም የሰው አእምሮ ተመራምሮ የማይደርስበት አምላካዊ ምስጢር ነው፡፡ ከተለወጠም በኋላ ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው ሥጋና ደም ይሆናል፡፡ ይህንንም ተቀብለን ከክርስቶስ ጋር አንድ አካል እንሆናለን፡፡

የካቶሊክ እምነት ደግሞ ‹‹ተፈጥሮአዊ በሆነ ለውጥ (Transubstantiation) የኅብስቱና የወይኑ ተፈጥሮ ወደ ሥጋና ደም ይቀየራል›› የሚል ነው፡፡ በእነርሱ እምነት ለውጡ በውጫዊ ገጽታውና በውስጣዊ ይዘቱ ላይ አይታይም፡፡ ተቀይሮም ሙሉ ክርስቶስን (ሥጋ፣ ደም፣ ነፍስና መለኮት ያለው) ይሆናል ብለው ያምናሉ፡፡ በሌላ በኩል ሉተራንስ ብሎ ራሱን የሚጠራው ዋናው የፕሮቴስታንት ክንፍ ስለ ቁርባን የሚያራምደው እምነት ‹‹ምስጢራዊ ኅብረት (Sacramental Union)›› ይባላል፡፡ ይህም የክርስቶስ ሥጋና ደም ከኅብስቱና ከወይኑ ጋር አብሮ በኅብረት ይገኛል የሚል ሲሆን የሚቀበሉትም ሥጋውና ደሙን እንዲሁም ኅብስቱንና ወይኑን አብረው ይቀበላሉ ብለው ያምናሉ፡፡

በአንጻሩ ተሃድሶአውያኑ ደግሞ ‹‹በመንፈስ መገኘት (Spiritual Presence)›› የሚል አስተምህሮ አላቸው፡፡ ይህም በቁርባኑ ላይ ክርስቶስ በአካል አይገኝበትም፤ በመንፈስ እንጂ የሚል ነው፡፡ ስለዚህም በኅብስቱና በወይኑም የሚካሄድ የተፈጥሮ/ይዘት ለውጥ የለም ብለው የሚያምኑ ሲሆን ከቁርባኑ ጋር ያለው መንፈስም የሚቀበሉትን ክርስቲያኖችን ከክርስቶስ ጋር ያገናኛቸዋል ይላሉ፡፡

ሌላው በቁርባን ላይ ያለው እምነት የተለያዩ አዳዲስ የእምነት ድርጅቶች የሚያራምዱት ‹‹መታሰቢያነት (Memorialism)›› የሚለው ነው፡፡ ይህም ኅብስቱና ወይኑ የክርስቶስ ሥጋና ደም መታሰቢያ ምልክቶች ብቻ ናቸው የሚል ትምህርት ነው፡፡ በዚህ መሠረት ኅብስቱንና ወይኑን የሚቀበል የክርስቶስን መታሰቢያ ያደርጋል የሚሉ ሲሆን ክርስቶስ በክርስቲያኖቹ ኅሊና እንጂ በኅብስቱና በወይኑ አይገኝም ብለውም ያስተምራሉ፡፡ በእነርሱ እምነት የቁርባን ሥርዓቱ ምልክትና መታሰቢያ ብቻ ነው፡፡ በመጨረሻም ቁርባን የሚባለው የእግዚአብሔር ቃል እንጂ የሚበላና የሚጠጣ አይደለም (Real Absence) የሚል አስተሳሰብ ያላቸው ወገኖችም አሉ፡፡ እኛ ግን አምላካችን ክርስቶስ ያስተማረውንና የሠራልንን የምስጢረ ቁርባን ሥርዓት መሠረት አድርገን በአማናዊው የክርስቶስ ሥጋና ደም (ነፍስ የተለየው መለኮት የተዋሐደው) እናምናለን፡፡

እውነት ለሁሉ

06 Dec, 11:04


እንዳትስቁ ዋ‼️‼️ 😂

“ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥
#ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ #የእግዚአብሔርን_መንግሥት_አይወርሱም።”
— ገላትያ 5፥21

እውነት ለሁሉ

06 Dec, 08:56


በድካማችን (ኃጢአት ሰርተን ስንወድቅ) የሚራራ ሊቀ ካህናት መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ከቸር አባቱ ጋር ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ውዳሴ አምልኮ ይኹንለት 🥰
«በሰማያት ያለፈ ትልቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን ጸንተን ሃይማኖታችንን እንጠብቅ።ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።»ዕብ 4፥14


«ሰው የሆነም ዘመድ ሊሆነን ብቻ ኣይደለም ፈጽሞ ይቅር አለን ኃጢአታችንን ለማስተስረይ ከአብ ጋር ለማስታረቅ ሊቀ ካህናትም ይሆነን ዘንድ ወደደ እንጂ ስለዚህም ሰዎችን ሊመስላቸው ይገባል፣ ባለው ነገሩ ላይ ጨምሮ በሁሉ አዛኝ የሕዝቡንም ኃጢአት ለማስተስረይ በእግዚአብሔር ዘንድ የታመነ አስታራቂ ይሆናቸው ዘንድ ነው ።

ባሕርያችንን ስለተዋሐደ ሰው የመሆኑን ነገር ያስተምረን ዘንድ ይኸን ተናገረ ሰው ለ መሆን ያበቃው ለማስታረቅ ኃጢአትን ለማስተስረይ ብቻ ነው እንጂ ሌላ ምክንያት የለውም። (ሃይማኖተ አበው ዘዩሐንስ አፈወርቅ 63:13-14)

………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!


ይቆየን

እውነት ለሁሉ

05 Dec, 18:04


وَهُوَ الَّذِي خَلَقَ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ فِي سِتَّةِ أَيَّامٍ وَكَانَ عَرْشُهُ عَلَى الْمَاءِ لِيَبْلُوَكُمْ أَيُّكُمْ أَحْسَنُ عَمَلًا ۗ وَلَئِن قُلْتَ إِنَّكُم مَّبْعُوثُونَ مِن بَعْدِ الْمَوْتِ لَيَقُولَنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا إِنْ هَٰذَا إِلَّا سِحْرٌ مُّبِينٌ

እርሱም ያ ሰማያትንና ምድርን በስድስት ቀኖች ውስጥ የፈጠረ ነው፡፡ ዐርሹም በውሃ ላይ ነበር፡፡ የትኛችሁ ሥራው ያማረ መሆኑን ይፈትናችሁ ዘንድ (ፈጠራቸው)፡፡ «እናንተ ከሞት በኋላ በእርግጥ ተቀስቃሾች ናችሁ» ብትልም እነዚያ የካዱት ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም ይላሉ፡፡ ሱራ 11፡7

                  VS


۞ قُلْ أَئِنَّكُمْ لَتَكْفُرُونَ بِالَّذِي خَلَقَ الْأَرْضَ فِي يَوْمَيْنِ وَتَجْعَلُونَ لَهُ أَندَادًا ۚ ذَٰلِكَ رَبُّ الْعَالَمِينَ

በላቸው «እናንተ በዚያ ምድርን በሁለት ቀኖች ውስጥ በፈጠረው አምላክ በእርግጥ ትክዳላችሁን? ለእርሱም ባለንጣዎችን ታደርጋላችሁን? ያ (ይህንን የሠራው) የዓለማት ጌታ ነው፡፡

فَقَضَاهُنَّ سَبْعَ سَمَاوَاتٍ فِي يَوْمَيْنِ وَأَوْحَىٰ فِي كُلِّ سَمَاءٍ أَمْرَهَا ۚ وَزَيَّنَّا السَّمَاءَ الدُّنْيَا بِمَصَابِيحَ وَحِفْظًا ۚ ذَٰلِكَ تَقْدِيرُ الْعَزِيزِ الْعَلِيمِ

በሁለት ቀኖችም ውስጥ ሰባት ሰማያት አደረጋቸው፡፡ በሰማይቱም ሁሉ ነገሯን አዘጋጀ፡፡ ቅርቢቱንም ሰማይ በመብራቶች አጌጥን፡፡ (ከሰይጣናት) መጠበቅንም ጠበቅናት፡፡ ይህ የአሸናፊው የዐዋቂው (ጌታ) ውሳኔ ነው፡፡ (የተብራሩት) ምዕራፍ ሱራ)41፡9-12

ሱራ 11ቁጥር ሰባት በ6ቀን "ሰመያትን" ና ምድርን ተፈጠረ ሲል
41ኛው ሱራ ምድር 2በሁለት ቀን ሰማያቶችም በሁለት ቀን ተፈጠሩ ይላል በአጠቃላይ 2+2=4 በአራት ቀን ሰማያትና ምድር ተፈጠሩ

የትኛው ነው ትክክል በ6ቀን ነው Vs በ4ቀን ¿



وَكَذَٰلِكَ أَنزَلْنَاهُ آيَاتٍ بَيِّنَاتٍ وَأَنَّ اللَّهَ يَهْدِي مَن يُرِيدُ

እንደዚሁም (ቁርኣንን) የተብራሩ አንቀጾች አድርገን አወረድነው፡፡ አላህም የሚሻውን ሰው ይመራል፡፡ የሐጂ ምዕራፍ ቁጥር 16

እውነት ለሁሉ

05 Dec, 17:49


ጂኒ ብሎ ጽፎበታል ሰው እንዴት ከወንድም እህቱ ይሸሻል 😂

እውነት ለሁሉ

05 Dec, 10:58


ቅዱስ ዮሃንስ አፈወርቅ

አየህ ጥምቀት ምን ያክል ጥቅሞች እንዳሉት ተገነዘብክ ?
አንዳንዶች ይህ ሰማያዊ ስጦታ የኃጢአት ስርየትን ብቻ እንደሚይዝ ያስባሉ።
እኛ ግን በጥምቀት ከአስር ያላነሱ ጥቅሞች እንደምናገኝ ዘርዝረናል...በዚህ ምክንያት ነው ህፃናትን የምናጠምቀው
ምንም እንኳ በኃጢአት የተጠቁ ባይሆኑም በጥምቀት በኩል  ቅድስናን ፣ፅድቅን ፣ ልጅነትን ፣ ርስትን ከክርስቶስ ጋር አንድነትን ይቀበላሉ በጥምቀትም የክርስቶስ አካል ይሆናሉ።

You see how many are the benefits of baptism, and some think its heavenly grace consists only in the remission of sins, but we have enumerated ten honors [it bestows]! For this reason we baptize even infants, though they are not defiled by [personal] sins, so that there may be given to them holiness, righteousness, adoption, inheritance, brotherhood with Christ, and that they may be his [Christ’s] members” (Baptismal Catecheses in Augustine, Against Julian 1:6:21 [A.D. 388]).

እውነት ለሁሉ

05 Dec, 10:50


origen 158 -253A.D

“The Church received from the apostles the tradition of giving baptism even to infants.

” (Commentaries on Romans 5:9 [A.D. 248]).

ቤተክርስቲያን ህፃናትን የማጥመቅ ስርዓት ከሐዋርያት ተቀብላለች።

” (Commentaries on Romans 5:9 [A.D. 248]).

እውነት ለሁሉ

05 Dec, 07:24


https://t.me/enibakom_apologetics

Join eyaderegachu እስልምና lay miserawen wendimachinin aberetatut ክርስቲያኖች

እውነት ለሁሉ

04 Dec, 21:25


እንደምታዩት ልጁ እኛ እያለ አላህ ስለሚጠራ በቁርአኑ ስላሴን ምናመልክ ያረጋሉ በማለት ነበር ሀሳቡን የመለሰው

ግን እሄ ስህተት ነው ሥላሴ እውነተኛ አምላክ ነው አንድ ልንሆን ይገባል እንጂ እናንተም ስላሴን ታመልካላችሁ ማለት እውነተኛውን አምላክ ታመልካላችሁ  ስለሆነ ብታመልኩ አንድ እንሆን ነበር እና ስላሴን ታመልካላችሁ አትባሉም

እንደዛ ካልሆነ ታዳ ምድነው ምትሉን ?? ካላችሁ እናንተ የሥላሴን አስተምህሮ ስለማትቀበሉ ምንላችሁ ብዙ አምላክ ታመልካላችሁ ነው ምንለው ስላሴ እና 3 የተለያዩ ስለሆኑ ለዛም ነው ሥላሴን ከቁጥርጋ አያይዛችሁ ማሰሙን ስለዚህ ብዙ አምላኪዎች ናችሁ ነው በአጭሩ አላህ እኛ ብሎ ስለሚጠራ

ሲቀጥል መልስ ብሎ ያመጣው አላህ አንድ በላይ ስላልሆነ አንድ አምላክ ነኝ ብሎ ስለተናገረ ብሎ ነው የዘረዘረው

እሄም ትክክል ማይሆኑበት ነጥቦች ይነሳሉ
እራሱን ለማክበር ሀያልነቱ ነው የተባለበት መልስ ማይሆንበት።
እንደ አርጊው ሚነሱት

1,ኛው እናንተ እንደምትሉን እርስ በእርስ ይጋጫል ሚል ሀሳብ ሊነሳል ያስችላል እናንተ በምትሉን ግጭት አንድ ነኝ ብሎ ተናግሮ መልሶ ከአንድ በላይ እንደሆነ አርጎ ስለተናገረ እርስ በርሱ ይጣረሳል። አንድኛው እሄ ነው

2,  እራሴን እያከበርኩ ነው ብሎ ስላልተናገረ መልስ አይሆንም እንደውም ክርስቲያኖችን ኢየሱስ አምላክ ነኝ ያለበትን ቃል በቃል አሳየኝ ብላችሁ እንደምታነሱት እኛም ተመሳሳዩን  መጠየቅ እንችላለን አላህ ቃል በቃል እኛ እያልኩ ማወራው እራሴን እያከበርኩ ስለሆነ ነው ያለበትን አሳይ ካላሳየህ አላህ ከአንድ በላይ ነው። በማለት መልሳችሁ ስህተት እንደሆነ እንዲሁም ከአንድ በላይ አምላክ ምታመልኩት በማለት አርጊውን እናንተ በምሞግቱን መሠረት መልሳችሁን እናፈርሳለን ማለት ነው

3ኛው ደሞ አላህ ሰው አልሆንም ፍጡር ሰው ስለሆነ አላህ አላህ ልጅ የለውም ፍጡር ልጅ ስላለው ብሎ መንፈሳዊነት በሌለው መልኩ ራሱን የሚገልጽ አላህ እኛ በማለት ደሞ ፍጡር በሚገልጽበት መግለጹ ቃሉን የአላህ ያፈርስበታል ወይም የመጀመሪያውን ማለት የለበትም አንድ ኢስላም ሚያምንበት ዶግማ ያረጋችሁትን ሰው አይሆንም አይወለድም ሰው ፍጡር ስለሆነ ሚለውን።
ወይም አላህ ሰው መሆን ይችላል ይወለዳል ይወልዳል ማለት ማመን አለባችሁ ፍጡር ራሳቸውን በሚገልጽበት እኛ በማለትስለገለጸ። ጠቅለል ሲል ፍጡር በሚገለጽበት መገለጽ አላህ ይወልዳል ይወለዳል በማለት መታመን አለበትአ በመንፈሳዊነት በሉት በምንም ምክንያቱም እኛ እያለ ፍጡር በሚገለጽበት ራሱን ስለገለጸ።
እንደ አርጊው እነዚን
--------------------------------------------------------
እንደ ቁርአኑ ደሞ >>
4,እናንተ እንዳላችሁት እንበል ብንል ያላችሁት መልስ እንደማይሆን አይተናል ግን እንደው ተቀብለናችሁ እራሱን ለማክበር ሀያልነቱን ብንል
ስለመርየም ኢሳን መውለዷ በተነገረበት ላይ

ከእነሱም መጋረጃን አደረገች። መንፈሳችንምም (ጂብሪልን) ወደርሷ ላክን፡፡ ለእርሷም ትክክለኛ ሰው ሆኖ ተመሰለላት፡፡19፡17 ላይ ተገልጿል
ከዚ ጥቅስ ላይ ሁለት ነጥቦች ይነሳሉ "አላህ" መንፈሳችን በመላት አላህ ብዙ መንፈስ እንዳለው ይገልጻል እሄም ብቻ ሳይሆን ያን ብዙ መንፈሶች ሚልኩ ብዙሀን አላሆች እንዳሉ ሲገልጽ ደሞ ላክን በማለት ብዙ መንፈሶችን ሚልኩ ብዙ አላሆች እንዳሉ ይገልጻል
ስለ አደምና እቢሊስ

በእርግጥም ፈጠርናችሁ፡፡ ከዚያም ቀረጽናችሁ፡፡ ከዚያም ለመላእክቶች «ለአዳም ስገዱ» አልን፡፡ ወዲያውም ሰገዱ፡፡ ኢብሊስ (ዲያብሎስ) ሲቀር ከሰጋጆቹ አልኾነም፡፡ 7፡11

እዚህም ላይ ልጁ ትልቅ መልስ አርጎ ያስቀመጠው የአምላክ ንግግሮቹን ነበር በሱራ 7ላይ የአምላክ ንግግሮችን መለኮታዊ ቀተጻፈበት ላይ አላህ ፈጠርን የፈጣሪ ባህሪን የብዙሀን የቁርአን አላሆች እንደሆነ ይገልጻል እሄም ብቻ ሳይሆን አደምንም የቀረጹት በአምላካዊ ንግግሮች ላይ ቀረጽን በማለት ትዕዛዙንም አልን በማለት ይጨርሳል

እንደሙስሊሞች ይሆናል ተብሎ በመገጣጠም ሳይሆን ከቁርአኑ ቃል በማውጣት ብዝሃነት በፈጣሪ ንግግሮቹ ላይ ተናግሯል መቅረጽ አደምን በመፍጠር በፈጣሪነቱም ብዙሀንን እንደሆነ ከአንድ በላይ አይተናል

መንፈሳችን በማለት በአምላክነቱ ላይ ያ አምላክ ሚሉት ሙስሊሞች መንፈሶች እንዳሉት የአላህ እነዚህን ብዙሃን መንፈሶች ሚልከው አላህ "ላክን" በማለት ብዙ የአላህ መንፈሶች የኖሩት አላህ እነዛን ብዙሀን መንፈሶች ሚልኩ ብዙ አላሆች እንዳሉ "ላክን" በማለት አኳር በአምላክነቱ ላይ ብዙነቱ ገልጸዋል

እንደ ቁርአኑም አነጋገር የቁርኑ አንቀጾች የተብራሩ እንደሆነ ሚገልጽ ሲሆን የተብራራውን አንቀጽ በሌላ አንቀጽ ማብራራት ደሞ ሌላ መዘዝ ጥያቄ ይዞ የሚመጣ ነው ሚሆነው

እውነት ለሁሉ

03 Dec, 19:45


በፎቶ ላይ እንደገለጸው አቃቤ ሙስሊም ነኝ ሚለው እንዳያችሁት የአጋንንትን እምነት እንደ መስፈርት ማስረጃ አርጎ ነው የያዘው ስለምን ስለፈጣሪ በጥቅሉ ስለፈጣሪ  ከባይብል የአጋንንትን ምስክርነት ስለፈጣሪ ማስረጃነት አርጎ አቅርቧል።

እሱ በሄደበት መንገድ እንሂድ እና አጋንንት አዎ የፈጣራቸው ፈጣሪ አንድ አምላክ እንዳለ ያምናሉ አንድ እንደሆነ ሚያምኑት ግን በምን መልኩ ነው ሚለውን በደብ ማየት ያስፈልጋል አጋንንት አንድ አምላክ እንዳለ ሚያምኑት አንድ እንደሆነ እንደ ክርስቲያኖች በሥላሴን አንድ አምላክነት ነው ወይስ እንደ ሙስሊሞች ስላሴን በማያምኑ ሆነው ነው?

የሙስሊሞች እምነት ምን ይላል ሱራ <<19፣91 አለረህማን ልጅ የለውም>> እንዲሁም የጌጣጌጥ ምዕራፍ ላይ አላህ ልጅ የለውም እንጂ ቢኖረው ከተገዢዎቹ መጀመሪያ መልእክተኛው እንደነበረ ይገልጻል ግን በጥቅሉ አላህ ልጅ የለውም አላህ ልጅ ስለሌለው ነው ሥላሴን ትምህርት የተቃወመው።
የስላሴን ትምህርት እንደማይቀበሉ የማይክዱት እውነታ ቢሆንም አላህ ልጅ የሌለው ስለመሆኑ ትንሽ እንጥቀስ በማለት ነው እንቀጥልና

ከዛ አቃቤ ሙስሊም ነኝ ሚለው ልጅ ስለፈጣሪ ማንነት ትክክለኛ አምላክነት መስፈርት ለማረግ ብሎ ወይም ማስረጃ ያመጣው የአጋንንትን እምነት ከባይብል ስለሆነ

እኛም በእሱ መንገድ ማስረጃና መስፈርት የአጋንንትን እምነት ይዘን ሀሳቡን አፍረስን ሥላሴን ትክክለኛ አምላክነት እናሳያለን ማለት ነው

“ኢየሱስንም ባየ ጊዜ ጮኾ በፊቱ ተደፋ በታላቅ ድምፅም፦ የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ፥ ከአንተ ጋር ምን አለኝ? እንዳትሣቀየኝ እለምንሃለሁ አለ።”
  ሉቃስ 8፥28” ፤ ማቴዎስ 8፥29

... ብዙ መጥቀስ ይቻላል አጋንንት እግዚአብሔር ልጅ እንዳለው ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ ያምናሉ❤️

ስለዚህ ወዳጃችን መስፈርት ብሎ እንዳስቀመጠው አጋንንትምኳ አንድ አምላክ አንድ እንደሆነ ሚያምኑት እንደ ሙስሊሞች ስላሴን በተቃወመ መልኩ ሳይሆን እንደ ክርስቲያኖች ሥላሴን በማመን ያለ የአምላክ አንድነት ነው ሚያምኑት እነማን አጋንንቶች

ስለዚህ ወገናችን ስለ እውነተኛ ፈጣሪ ምስክርነት ብለህ ባመጣህው መሠረት የአጋንንቶችን ምስክርነት የአጋንንቶች እምነት  ደሞ
እንደ ክርስቲያኖች ሥላሴን በማመን መልኩ ስለፈጣሪ አንድነት ሚያምኑ የሆኑ እንጂ አንተ እንዳልከው አቃቤ ሙስሊሙ እንደሙስሊሞች ሥላሴን ተቃውመው ስላልሆነ ባንተ መስፈርት ብለህ ባስቀመጥከው መሠረት አላህ ፈጣሪ አደለም የክርስቲያኖች ሥላሴ አምላክነት ነው እውነተኛ ፈጣሪ
እሄ ያንተ ሙግት ስለሆነ ሥላሴ እውነተኛ አምላክ እንደሆነ ባፈልግም አምነሀል ወይም ተሳስቼ ነው ይቅርታ በል ካላልክ ባልከው መስፈርት ትክክል ነኝ እያልክ ስለሆነ በመስፈርትህ መሠረት ማስረጃ ባረከው መሠረት እውነተኛ አምላክ ሥላሴ ነው

በመጨረሻም ያልካትም ቃላት ክርስቲያኖችን ለናንተ ይሆናል ትክክለኛው ቦታ ላይ ሆነ ማለት ነው ሙስሊሞች ከሰይጣን የበለጣችሁ ባቀረብከው argument አፈሙዙ ወዳንተ ዙሮ ጠማማዎች ናችሁ እንዳልከው 😊

እውነት ለሁሉ

18 Nov, 18:34


ይህ ጥቅስ አባቶች ምን አሉ

“ሰው በእምነት ብቻ ሳይሆን #በሥራ እንዲጸድቅ ታያላችሁ።”
         — ያዕቆብ 2፥24

ሰው ስለ አመነ ብቻ አይጸድቅመም።እምነቱን በሥራ መግለጽ መቻል አለበት ምክንያቱም የእምነቱ ማረጋገጫው ሥራው ነው።#ራዕይ_22:12 ጌታ ሲመጣ እንደ #ሥራችን ዋጋችንን ይከፍለናል።

“በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።”
  — ማቴዎስ 7፥21
" እስከ መጨረሻው የሚፀና እርሱ ይድናል "
         ማቴ 24:13

#ቅዱስ_ቀሌምንጦስ_ዘሮም ለቆሮንቶስ ሰዎች በጻፈው ደብዳቤ ላይ

#St.Clement of Rome :Letter to the corinthians
     First epistle chapter 30
"ራሳችንን በመግዛት ተስማምተን ትህትናን እንልበስ ከሹክሽክታና ከስድብ ሁሉ ርቀን ቆመን በቃላችን ሳይሆን #በሥራችን እንጽደቅ"

     First epistle chapter 34
"ስለዚህም በመልካም #ሥራ ሰነፍች እንዳንሆን በፍጹም ልባችን ይመክረናል"

#St.Justin Martyr
      The First Apology chapter 16

"እርሱ እንዳስተማረው ሲኖሩ ያልተገኙትን የክርስቶስን ትዕዛዝ በአፋቸው ቢናገሩም ክርስቲያን  እንዳልሆኑ ይረዱ።#ሥራን የሚሰሩት እንጂ #የሚያምኑ አይደሉምና እንደ ቃሉ ይድናሉ"

#St.Ignatius
       Epistle to the Ephesians chapter 14

"ዛፍ በፍሬው ይገለጣል(ማቴ 12:33) ክርስቲያን ነኝ የሚሉ ሰዎች #በሥራቸው ይታወቃሉ።ሰው እስከ መጨረሻው  በእምነት ፀንቶ ይገኝ እንጂ #በሥራው ብቻ አይፈለግም"

እውነት ለሁሉ

18 Nov, 14:52


ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ነው?
ለዋሒድ የተሰጠ ምላሽ
በኒቂያ ጉባኤና ለተጠየቁ ጥያቄዎች ምላሽ!
በዲያቆን ሸዋፈራው

ቻናሉን ተቀላቅለው በክርስትና ዙሪያ ለሚነሱ እስላማዊ ጥያቄዎች በቂ መልስ ያግኙ!
ለእስልምና ጥያቄዎች ክርስቲያናዊ መልሶች
https://t.me/Jesus_is_God_Maedot

እውነት ለሁሉ

18 Nov, 07:00


እፎይ አካውቱ ተዘግቷል አዘግተውታል እዚ ያላችሁ አዲሱን ኮፒሊክ ፎሎና ሼር ሪፖስት እያረጋችሁ

https://vm.tiktok.com/ZMhtGcmW6/

እውነት ለሁሉ

17 Nov, 20:05


ሙስሊሞች የገሀነብ ናቸው 😢
በመጀመሪያ እስልምና ክርስትናን በመቃወም የተነሳ ነው ከዚ በፊትም የሰይጣን ትምህርት እንደሆነ በእስልምናው አስተምህሮ ውስጥ አይተናል መልሼ ፎርዋርድም አረግላችኃለሁ
ዛሬ ግን ምናየው እስልምና መጨረሻው ሲኦል እሳት እንደሆነ ነው

እስልምናው ከዚህ አለም በኃላ ወዳኛው አለም ላይ ቅርቢቱ ይለዋል ቁርአኑ የቅርቢቱ ሕይወት እሄን አለም ከዚ አለም በኃላ ያለውን ማግባት መጋባት የለም ሚለውን ጥሶ ወንድ ከሴትጋ ግንኙነት ያረጋል የወይን ጠጅም ይጠጣል ሚል እምነት አለው በቪዲኦም ማቅረብ ይቻላል የማይካድ እውነታ ስለሆነ የወይን ጠጅ ይጠጣሉ

መጽሀፍ ቅዱስ ለአውሬው ሚሰግዱትን አማኝ ያልሆኑትን በመጨረሻ ቅጣት አላቸው እርሱም በእሳት በሲኦል መቀጣል ነው የንስሐ እድሜአቸውን ስላልተጠቀሙ እና በእሳት መቃጠሉን ባይብል ምን ይለዋል የወይን ጠጅ ይጠጣሉ ከሞት በኃላ ስላለው ፍርዱን አማኝ ያልሆኑትን የወይን ጠጅ ይጠጣሉ ይላል እሄም የወይን ጠጅ በእሳት መቃጠልና የእግዚአብሔር ቁጣ መሆኑን ሚገልጽ ነው እሄው

ራእይ 14
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¹⁰ እርሱ ደግሞ በቍጣው ጽዋ ሳይቀላቅል ከተዘጋጀው ከእግዚአብሔር ቍጣ ወይን ጠጅ ይጠጣል፥ በቅዱሳንም መላእክትና በበጉ ፊት በእሳትና በዲን ይሳቀያል።
ይህ የወይን ጠጅ ቅጣትና በእሳት ዲን መቃጠል ነው። እንዳየነው
የእስልምናው ደሞ አማኞቾ በገነት የወይን ጠጅ ይጠጣሉ ይላል
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡ የተሰላፊዎቹ ምዕራፍ 45 ላይ
ስለዚህ ምን ይመስላችኃል የወይን ጠጅ ይጠጣሉ ቁጣውን በእሳት ዲን እየተቃጠሉ ሚለውን የባይብል ሀሳብን

እስልምናው አማኞች መስሊሞች የወይን ጠጅ ይጠጣሉ ማለቱ የእሳት ዲኑን እንደሆነ አያመላክትም መጽሐፍ ቅዱስ የወይን ጠጅ ቁጣውን ይጠጣሉ የእሳት ዲንም ይቃጠላሉ ብሎ ያነሳውን ቁርአን ደሞ አማኞቼ የወይን ጠጅ ይጠጣሉ ማለቱ አላህ የገሀነብ መሆኑን እና እናንተንም ይዟችሁ ለማስገባት እንደሆነስ አያመላክትምን

ለሙስሊማኑ እሄን ቻሌጅ ከእራሳችሁ ጋር  ተሟገቱ አስተውሉ ራዕይ መጽሀፍ ደሞ ትንቢቱ ሚለው ተፈጻሚ መሆኑን አትርሱ ከዛሬ 2000 አመት በፊት ስለ 666 ተናግሮና ተንብዮ በዚህ ዘመን በኛም ሰይጣን ምልክቱን 666 ብሎ በአይኖቻችን ያየነውን የሰማነውን አስቀድሞ የተናገረ ትልቅ መጽሀፍ ነው

እና በጀነት የወይን ጠጅ እሳትና ዲን የፈጣሪ ቁጣ ነው
አላህ ደሞ የወይን ጠጅ አለ እያለ ነው ስለዚህ አላህ የሲኦል የገሀነብ ሆኖ ጀነት በሚል ማታለያ ገሀነብ ሊያስገባችሁ መሆኑን ትንሽስ አልተገለጠላችሁም ቻሌጁን ተቀላቀሉ ሙስሊሞች የሕይወት ጉዳይ ነው ለምቶዷቸው ሙስሊሞች ሼር አርጉላቸው መጽሀፉ ባታምኑበትም ቃሉ ተፈጻሚ እውነታ መሆኑንም ከግምት አስገቡ በጀነት የወይን ጠጅ የለም
እግዚአብሔር በአንድም በሌላ ይናገራል አስተውሉ 🙏

እውነት ለሁሉ

17 Nov, 18:23


ወነአምን በአሐቲ ጥምቀት ለሥርየተ ኃጢአት" ጸሎተ ሃይማኖት
"We confess one baptism for the remission of sins" Nicene- Constantinopolitan Creed
“ጴጥሮስም፦ ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።”ሐዋ 2፥38
“አሁንስ ለምን ትዘገያለህ? ተነሣና ስሙን እየጠራህ ተጠመቅ ከኃጢአትህም ታጠብ።” ሐዋ 22፥16
“አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤”ኤፌ 4፥5
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

ይቆየን

እውነት ለሁሉ

17 Nov, 13:02


ሲመስለኝ የወረደበት ምክንያት እሄ አያ
በዛ ሰአት ምግብ ካላሳዮቸው የማይሰሙ በጣም ምግብ ሚወዱ  ሰዎች ኑረው ይመስለኛል ከሞታችሁ በኃላ ትመገባላችሁ ህያዉ ሁናችሁ ያለበት

ምክንያቱም ቁርአን ለእውነት ሳይሆን ለሰው ሕሊና ሚጨነቅ ስለሆነ እንዳየሁት ቁርአኑን 👀

እዚ ያላችሁ ሙስሊሞች ግን ጎበዝ ናችሁ እንደ ቲክቶከሮቹ ሙስሊሞች አሸመጥጡም 🤚
ወደ እውነተኛው ሃይማኖት ምትዘነበሉበት ቀን እናፍቃለው ለምን ብትሉ ቁርአንን አንብቤ የፈጣሪ ቃል እኳ ልል ደህና የተማረ ሰው ጽሁፍ ነው ብዬ ማመን ስላቃተኝ

በቀጣይ በክርስትናው አስከፊ ተብሎ የተገለጸበትን "ቃል" ቁርአን በአላህ ያመነ ሰው ሚያገኘው ቆጆ ነገር መሆኑን የተናገረበትን አንቀጽ አሳያችኃለው

እውነት ለሁሉ

17 Nov, 11:10


ጉድኮ ነው 😂😁 መጽሀፍ ቅዱስ ያመኑትን ሕያዋን ናቸው ሙታን አደሉም ሲል የሰማው የቁርአኑ ባሌቤት አላህ ሆዬ 😁

በአላህ መንገድ የተጋደሉትን ሙታን አርገህ አትገምታቸዎ እሺ ከዛስ ስለው እነሱ በጌታቸው ዘንድ ሕያዋን ናቸው ብሎ   ምን ቢል ጥሩ ነው ሕያዋን ናቸው ይመገባሉ 🙈
ስለዚህ ቁርአን ስለ ሕያውነት በደብ አጣርቶ ሳይዝ ለዚህ ስህተት ተዳርጓል ሕያዋን ናቸው ሲባልኮ ከሞቱ በኃላ ይመገባሉ ማለት አደለም  🤭 አላህ ሆዬ ቀጥታ ሕያውነትን ከመብላትና ከመጠጣትጋ አያይዞ ነው የተናገረው  🙄


وَلَا تَحْسَبَنَّ الَّذِينَ قُتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ أَمْوَاتًا ۚ بَلْ أَحْيَاءٌ عِندَ رَبِّهِمْ يُرْزَقُونَ

እነዚያን በአላህ መንገድ የተገደሉትን ሙታን አድርገህ አትገምታቸው፡፡ በእርግጥ እነርሱ እጌታቸው ዘንድ ሕያዋን ናቸው፤ ይመገባሉ፡፡3:169

እውነት ለሁሉ

17 Nov, 10:32


እስቲ የኔ ተወዳጆች አንድ ነገር ላስቸግራቹ አሪፍ የአባቶችን ትምህርት ምታገኙበትን ቻናል ልጠቁማቹ

https://t.me/Orientalchurch

join በማለት የአባቶችን ትምህርት እንድታቁ ሚጠቅማቹ ጥሩ ቻናል ነው ጆይን በሉት ❤️❤️

እውነት ለሁሉ

17 Nov, 10:30


ለአብርሃም የተገለጠው ማን ነው??

#ዘፍጥረት 18
¹ በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት።
² ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ፤ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ፥እንዲህም አለ፦

**ለአብርሃም እግዚአብሔር በምን መልኩ ነው የተገለጠለት እንደው አብርሃም እግዚአብሔር አይቶታል ማለት ነው። በሌላ ቦታ ደግሞ "ሰው አይቶኝ አይድንምና ፊቴን ማየት አይቻላቹም"ስለዚህ እግዚአብሔር ማንም ማየት አይችልም።
በምን መልኩ ነው እግዚአብሔር አምላክ ለአብርሃም የተገለጠለት ካልን በመላእክት በኩል አብርሃም ያየው ሦስት ሰው ነው እዚህ ጋር ሰው ነው የሚለው እኮ መላእክት አይልም የሚል ሃሳብ ሊነሳ ይችላል።እና መላእክት በሰው አምሳል ሊገለጡ ይችላሉ ለምሳሌ

“ገናም በጸሎት ስናገር አስቀድሜ በራእይ አይቼው የነበረው ሰው ገብርኤል እነሆ እየበረረ መጣ፤ በማታም መሥዋዕት ጊዜ ዳሰሰኝ።”
     #ዳንኤል 9፥21
**ስለዚህ መላእክት በሰው አምሳል ሊገለጡ ይችላሉ።
ለአብርሃም የተገለጠለት ቅድስት ሥላሴ በመላእክት በኩል ነው ማለትም ሦስት መላእክት መተው ይቆማሉ ቅድስት ሥላሴ ደግሞ አብርሃምን ያነጋግሩታል።አብርሃም ባያቸው ጊዜ ሮጦ ሰገደ የሰገደው ለቅድስት ሥላሴ ነው።

#ዘፍጥረት 18
³ አቤቱ፥ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤
⁴ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ፤
⁵ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት"

**አብርሃምም እንደ አንድ እንደ ብዙም ያናግራቸዋል "አቤቱ በፊትህ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምንሃለሁ"ሲል በነጠላ እንደ አንድ ይናገራል ቀጥሎ አብዝቶ ሲናገር እንመለከታለን “ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ “ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ፤ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት።” ብዛታቸውን ማለትም የአካል ሦስትነታቸውን ያሳያል ግን እዚህ ጋር ወደ "ወደ ባሪያቹ መጥታችኋልና" ሲል እግዚአብሔር እና መላእክት ባንድ ላይ ባሪያቹ ተብሎ አይነገርም ያለው በሦስት አካላት ለተገለጠለት ለእግዚአብሔር ነው  ወደ ታች ዝቅ ብላቹ ስታነቡ ሁለቱ ሰዎች ወደ ሰዶም እንደሄዱ ግልጽ ያደርገዋል

“ሰዎቹም ከዚያ ፊታቸውን አቀኑ፥ ወደ ሰዶምም ሄዱ፤ አብርሃም ግን በእግዚአብሔር ፊት ገና ቆሞ ነበር።”
     #ዘፍጥረት 18፥22

#አውግስጢኖስ ይህን ሁለቱ የሄዱትን እንዚህ ይላል ከአብርሃም ጋር የቆየው #አብ ነው። ሁለቱ ሰዎች የሄዱት #ወልድ እና #መንፈስ ቅዱስ ናቸው በመፅሐፍ ስናነብ አብ አንድም ቦታ ተላከ የሚል አናገኝም ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ እንደተላኩ ብዙ ቦታ ተነግሯል ይላል ።
ወደ ሰዶም የሄዱት ወልድና መንፈስ ቅዱስ ናቸው በምን እናውቃለን ካልን
“ሁለቱም መላእክት በመሸ ጊዜ ወደ ሰዶም ገቡ፤ ሎጥም በሰዶም በር ተቀምጦ ነበር። ሎጥም ባያቸው ጊዜ ሊቀበላቸው ተነሣ፤ ፊቱንም ደፍቶ ወደ ምድር ሰገደ፥ አላቸውም፦”
         #ዘፍጥረት 19፥1
**መላእክት የተባሉት ወደ ሰዶም ገቡ

“እኛ ይህን ስፍራ እናጠፋለንና፥ ጩኸታቸው በእግዚአብሔር ፊት ትልቅ ሆኖአልና፤ እናጠፋውም ዘንድ እግዚአብሔር ሰድዶናል።”
        #ዘፍጥረት 19፥13
**ሁለቱ መላእክት የተባሉት ሊያጠፉ ከእግዚአብሔር ዘንድ እንደተላኩ የተላኩ መሆናቸውን እንረዳለን
ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ መሆናቸውን ማወቅ እንችላለን ብዙ ቦታ በቅዱሳን መፅሐፍ እንደተላኩ ተገልጿል

#ዘፍጥረት 19
¹⁸ ሎጥም አላቸው፦ ጌታዬ ሆይ፥ እንዲህስ አይሁን፤
¹⁹ እነሆ ባሪያህ በፊትህ ሞገስን አግኝቶአል፥ ነፍሴን ለማዳን ያደረግህልኝን ምሕረትህንም አብዝተሃል፤ ክፉ እንዳያገኘኝና እንዳልሞት ወደ ተራራ ሸሽቼ አመልጥ ዘንድ አልችልም፤

** "ሎጥም አላቸው ጌታዬ ሆይ እንዲህ አይሁን" አማርኛ ላይ ጌቶቼ ይላል ሌሎች መፅሐፍ እንግሊዘኛ መፅሐፍ ላይ ደግሞ በብዛት ጌታዬ ይለዋል የሰባ ሊቃናቱም ዕብራይስጡም ጌታዬ ነው የሚለው ሎጥም አላቸው ሲል በብዛት ሲናገር እናያለን ሁለቱንም በአንድ ላይ ጌታዬ ብሎ በነጠላ ሲናገር እንመለከታለን ሎጥ ቀጥሎም
መላእክት ሳይሆኑ እግዚአብሔር እንደሆነ መለየት እንችላለን "ነፍሴን ለማዳን ያደረክልኝን ምህረትህንም አብዝተሃል"በማለት ነፍስን ማዳን የሚችል ምህረትን የሚያደርግ ከእግዚአብሔር ውጭ ማን አለ።

እግዚአብሔርም በሰዶምና በገሞራ ላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ከሰማይ እሳትና ዲን አዘነበ፤”
     #ዘፍጥረት 19፥24
**ማን ከማን ዘንድ እግዚአብሔር ከእግዚአብሔር ዘንድ መላእክት ቢሆኑ ኖሮ መላእክት እግዚአብሔር ተብሎ አይነገርላቸውም

ወልድ ከሁለት መላእክት ጋር ተገለጠለት የሚሉ አባቶች አሉ።
ይህ የአባቶች እይታ ነው

#st.Augustine On the Trinity Book 2
chapter 10,11,12

#St.Augustine   City of God Book 16 chapter 29

እውነት ለሁሉ

17 Nov, 10:26


አላህ ያጠመመውን ሰይጣንን(ኢብሊስን) ማን ሊያቃናው ይችላል?ሰይጣን(ኢብሊስ) ራሱ በቁርዐን አላህ ነው ያጠመመኝ ሲል በግልጽ ተናግሯልና.......😁 ለኢብሊስ መጥመምና ሰዎችን ማጥመም ተጠያቂው የቁርዐኑ አላህ ወይስ ኢብሊስ?????

قَالَ رَبِّ بِمَا أَغْوَيْتَنِي لَأُزَيِّنَنَّ لَهُمْ فِي الْأَرْضِ

 وَلَأُغْوِيَنَّهُمْ أَجْمَعِينَ

(ኢብሊስ/ሰይጣን) አለ «ጌታዬ ሆይ! እኔን በማጥመምህ ይኹንብኝ ለነርሱ በምድር ላይ (ኀጢአትን) እሸልምላቸዋለሁ፡፡ ሁሉንም አጠማቸዋለሁም፡፡»Sura Al-Hijr 15, Ayah 39

" የአላህ መልእክተኛ” ” ኹጥባቸው ላይ እንዲህ ይሉ ነበር፦ አላህን አመስግነዉ ለምስጋናዉ ተገቢ በሆነዉ መልኩ ካመሰገኑ በኃላ አላህ የመራውን ማንም አያጠመውም ፤ አላህ ያጠመመውን ማንም አያቀናውም። ከንግግር ሁሉ በላጩ የአላህ መጽሐፍ ነው፤ ከመመሪያ ሁሉ በላጩ
የሙሐመድ መመሪያ ነው። ከሁሉ የተጠላ ነገር ቢድዓ ነው፤ ቢድዓ ሁሉ ጥመት ነው፤ ጥመት ሁሉ በእሳት ነው።"ሡነን ነሣኢ : መጽሐፍ 19, ሐዲስ 23 ጃቢር ኢብኑ ዐብደላህ እንደተረከው
ﻋَﻦْ ﺟَﺎﺑِﺮِ ﺑْﻦِ ﻋَﺒْﺪِ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻗَﺎﻝَ ﻛَﺎﻥَ ﺭَﺳُﻮﻝُ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﺻَﻠَّﻰ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﻭَﺳَﻠَّﻢَ ﻳَﻘُﻮﻝُ ﻓِﻲ ﺧُﻄْﺒَﺘِﻪِ ﻳَﺤْﻤَﺪُ ﺍﻟﻠَّﻪَ ﻭَﻳُﺜْﻨِﻲ ﻋَﻠَﻴْﻪِ ﺑِﻤَﺎ ﻫُﻮَ ﺃَﻫْﻠُﻪُ ﺛُﻢَّ ﻳَﻘُﻮﻝُ ﻣَﻦْ ﻳَﻬْﺪِﻩِ ﺍﻟﻠَّﻪُ ﻓَﻠَﺎ ﻣُﻀِﻞَّ ﻟَﻪُ ﻭَﻣَﻦْ ﻳُﻀْﻠِﻠْﻪُ ﻓَﻠَﺎ ﻫَﺎﺩِﻱَ ﻟَﻪُ ﺇِﻥَّ ﺃَﺻْﺪَﻕَ ﺍﻟْﺤَﺪِﻳﺚِ ﻛِﺘَﺎﺏُ ﺍﻟﻠَّﻪِ ﻭَﺃَﺣْﺴَﻦَ ﺍﻟْﻬَﺪْﻱِ ﻫَﺪْﻱُ ﻣُﺤَﻤَّﺪٍ ﻭَﺷَﺮُّ ﺍﻟْﺄُﻣُﻮﺭِ ﻣُﺤْﺪَﺛَﺎﺗُﻬَﺎ ﻭَﻛُﻞُّ ﻣُﺤْﺪَﺛَﺔٍ ﺑِﺪْﻋَﺔٌ ﻭَﻛُﻞُّ ﺑِﺪْﻋَﺔٍ ﺿَﻠَﺎﻟَﺔٌ ﻭَﻛُﻞُّ ﺿَﻠَﺎﻟَﺔٍ ﻓِﻲ ﺍﻟﻨَّﺎﺭ"
ቻናሉን ተቀላቅለው በክርስትና ዙሪያ ለሚነሱ እስላማዊ ጥያቄዎች በቂ መልስ ያግኙ!
ለእስልምና ጥያቄዎች ክርስቲያናዊ መልሶች
https://t.me/Jesus_is_God_Maedot

እውነት ለሁሉ

16 Nov, 11:10


ቻናሉን ተቀላቅለው በክርስትና ዙሪያ ለሚነሱ እስላማዊ ጥያቄዎች በቂ መልስ ያግኙ!
ለእስልምና ጥያቄዎች ክርስቲያናዊ መልሶች
https://t.me/Jesus_is_God_Maedot

እውነት ለሁሉ

14 Nov, 16:56


እስራኤል ሱላማጢስ ከሞተ በኩር ተርፈው ከግብጽ ባርነት ወደ ከነዐን በበጉ መሥዋዕት እንዲመለሱ ፤አማናዊቷ ሱላማጢስ ድንግል ማርያም ኹላችንን የሚዋጀን የዓለሙን ኃጢአት የሚያስወግደውን (ዮሐ1፡29) የእግዚአብሔርን በግ ታቅፋ ከተሰደዱበት ከግብፅ ወደ እስራኤል ተመለሰች ለዚኽም ሰሎሞን ምልሰቷን አስመልክቶ “አንቺ ሱላማጢስ ሆይ፥ ተመለሽ፥ ተመለሽ፤ እናይሽ ዘንድ ተመለሽ፥ ተመለሽ። ”መኃል 7፥1 ሲል በምሥጢር ተቀኘ.....እኛም ድንግል ኾይ የታቀፍሽውን መድኃኒት ይዘሽ ወደ ሕይወታችን ተመየጢ ተመየጢ እንበላት........እርሷም ከከበረው ልጇ ኢየሱስ ጋር ወደ ኃጢአተኛው ሕይወታችን ትመለሳለች 🥰

"ሄሮድስም ከሞተ በኋላ፥ እነሆ፥ የጌታ መልአክ በግብፅ ለዮሴፍ በሕልም ታይቶ፦
የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፥ ሕፃኑን እናቱንም ይዘህ ወደ እስራኤል አገር ሂድ አለ። እርሱም ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ያዘና ወደ እስራኤል አገር ገባ።"ማቴ 2፡20-21

………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

ይቆየን

እውነት ለሁሉ

14 Nov, 11:19


‹‹ልብሱን ብቻ የዳሰስኹ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ›› ማቴ 9፡21
ጊዜው አብዛኛው ማኅበረሰብ በጨለማ ፤ ተስፋ በመቁረጥ እና በአጋንንት እስራት ውስጥ የነበረበት የዛሬ ሁለት ሺህ ዓመት ገደማ ነበር ወቅቱ በኃይልና በስልጣን ሙታንን የሚያነሳ ፤ ጎባጣን የሚያቀና ፤ ሽባን የሚተረትር ፤ ዕውራንን የሚያበራ ፤ ከአጋንንት እስራት የሚፈታ ፤ በበሽታ በደዌና በሰይጣን ላይ ስልጣን ያለው በጥቂት እንጀራና አሳ ብዙሃኑን የሚመግብ ብርቱ መሲህ ኢየሱስ እንደተነሳ በመንደሩ በሃገሩ ሁሉ የሚወራበት በችግር ላይ ያሉ በርሱ ለመዳን የሚመኙበት ነፍሳት አጥብቀው እርሱን የሚሹበት ጊዜ ነበር፡፡
በእርሱ ለመዳን ከሚመኙ ህሙማን መካከል 12 ዓመታት ሙሉ ያለማቋረጥ ደም ሲፈሳት ብዙዎች ተፀይፈዋት ርቀዋት እና ሸሽተዋት በሽታዋም ከኃጢአቷ የመነጨ እንደሆነ አስበው እንደ እርኩስ ይቆጥሯት ይነቅፏት የነበረች አንዲት ሴት ነበረች፡፡ ባለ መድኃኒቶችን ጎብኝታ ፤ ብዙ ሐኪሞችን አማክራ ገንዘቧን ከስክሳ (ማር5፡26) ለደዌዋ መፍትሄ ለበሽታዋ ፈውስ አላገኘችም፡፡ ተስፋ ቆርጣ ለብቻዋ በቤቷ ተቆራምዳ ረዳት አጥታ በለቅሶና በሐዘን በእንባና በችግር ትኖር በነበረበት በእለታት በአንደኛው ቀን ሰዎች ሁሉ ስለ እርሱ የሚያወሩለት ስለ መሲሁ ጌታ ኢየሱስ በወሬ በወሬ ሰማችና ከተጣለችበት አልጋ ተስፋ ከቆረጠችበት ቤቷ በፍጥነት ተነስታ ወደ አዳኟ መገስገስ ጀመረች፡፡
ታላቁ መሲህ ኢየሱስ በሚያልፍበት መንገድ ሁሉ ከሚከተሉት ሰዎች ብዛት የተነሳ ሁካታ ፤ ግርግር እና ግፊያ የበዛበት ሐዋርያቱም ማንም ወደ እርሱ እንዳይቀርብ የሚከለክሉበት ነበር፡፡ይሄ ሁሉ ግፊያ ሳያግዳት ፤ ግርግሩ ተስፋ ሳያስቆርጣት ፤ የሐዋርያቱ ክልከላ ሳያስቆማት ፤ የሰዉ መጠየፍ ግድ ሳይሰጣት እየወደቀች እየተነሳች ጌታዋ አዳኝዋ የሥጋና የነፍስ መድኃኒት ወደሆነው መሲህ ኢየሱስ ደረሰች ቃል ማውጣቱን ሳትጠብቅ ፤ በእጆቹ እንዲዳስሳት ሳትጠይቅ ‹‹ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ›› ማቴ 9፡21 በማለት በእምነት ቀርባ ምናልባት ልብሱን ዳሰው የዳኑ አብነቶች(እማኞች) መኖራቸውን ሳታነብ ሳታይ ‹‹በሰዎች መካከል መጥታ ልብሱን ዳሰሰች›› ማር5፡27 በዚህ ጊዜ የ አስራ ሁለት ዓመታት ሙሉ ሲያስጨንቃት ፤ በሰው ዘንድ እንድትጠላ አድርጎ ብቻዋን ያስቀራት ክፉ ደዌ ደም ‹‹ወዲያውም የደምዋ ምንጭ ደረቀ ከሥቃይዋም እንደዳነች በሰውነትዋ አወቀች››የዚህች ሴት እምነት ታላቅ ነበር ፡፡ ከእምነቷ ጽናት የተነሳ የተጠየፏትን ፤ የሚያንቋሽሻትን ፤ የሚተፋና የሚሰድባትን ሳትሰማ ጋሬጣውን አልፋ አጥሩን ሰባብራ በእምነት አልፋ የጌታ ኢየሱስን ልብስ ዳስሳ የ12 ዓመታት ችግሯ ተቀረፈላት ጋሬጣዋ ተሰበረላት ስብራቷ ተጠገነላት፡፡
ወዳጆቼ በሐዘን ፤በድካም ፤ ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ፤ በጭንቀት ፤ በመከራ ፤ በበሽታና በስቃይ ያላችኹ በእምነት ኢየሱስ ኾይ የልብስኽኝ ጫፍ ዳስሳ የተፈወሰችውን ሴት አድርገኝ በሉት፡፡ ያለመጠራጠር በእምነት ኾናችሁ ልንካኽ ከአንተም ኃይል ወጥቶ ይፈውሰኝ ፤ መከራዬን ያርቅልኝ ነቀፌታዬን ያስወግድልኝ በሉት ፡፡እርሱ ለድካማችን ብርታት ፤ ለማጣታችን ማግኘት ፤ ለበሽታችን ፈውስ ፤ ለጭንቀታችን መፍትሔ ፤ ሰላም ለማጣታችን ሰላም ፤ ለመከራችን እረፍት ነው፡፡ ጌታ ኢየሱስ ብሎ ያፈረ አንዳች የለም ፤ ስሙን ጠርቶ የወደቀ ማንም የለም ለዚህም ነው ቤተክርስቲያናችን ፡-
“ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም ለዘይጼውዖ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብስተ ሕይወት ለዘይበልዖ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ጽዋዐ መድኀኒት ለዘይሰትዮ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በግዐ መድኀኒት ለዘይሠውዖ ከመ ይባርኩነ ይፈኑ አርዳኦ ለጸባኢነ ይጽብኦ ወልታሁ ነሢኦ”
‹‹ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠራው ስሙ ጣፋጭ ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚበላው የሕይወት እንጀራ ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠጣው የመድኃኒት ጽዋ ነው፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚሠዋው የድኅነት በግ ነው፤ ይባርኩን ዘንድ ደቀ መዛሙርቱን ይላክ፤ ጋሻውን አንሥቶ የሚጣላንን ይጣላው››ተአምረ ኢየሱስ
እያለች የምታመሰግነው ፡፡ ይሄ መድኃኒት ስሙ ፈዋሽ ቀዳሽ ፤ ሥጋው የሕይወት መብል ደሙ የሕይወት መጠጥ ነው፡፡ስሙን አብዝተን እንጥራው ፈውሰኝ አድነኝ እንበለው እርሱም “እርሱ ራሱ አልለቅህም፣ ከቶም አልተውህም ብሎአልና” ዕብ 13፡ 5 አይተወንም አይጥለንም ፡፡ጌታ፣ እርሱ ራሱ፣ አልተዋችሁም ስላለን፣ ‹‹አድነን›› ባልነው ጊዜ፣ ጩኸታችንን ስለሰማልን፡ ስለራራልን፣ ከምናውቀውና ከማናውቀው፣ ከምንገምተውና ከማንገምተው ውርደት እና ጉድ ሁሉ ጠብቆን፣ እነሆ ዛሬን ለማየት በቃን።
አባት ሆይ፣ የልመናችንንን ድምጽ ሰምተሃልና እንወድሃለን፤ ጆሮህን ወደ እኛ አዘንብለሃልና በሕይወት ዘመናችን ሁሉ ስምህን እንጠራለን (መዝ 116)። አላሳፈርከንም፣ ሞት ሲገባን ሕይወትን ሰጠኸን፣ ውርደት ሲጠብቀን በክብር አቆምከን፣ መጠጊያ እና መሸሸጊያ ሁነን ባልንሕ ጊዜ ሁሉ ከጠላት ክፋትና አመጻ ሰውረኸናልና ተመስገን። ምስጋናችን ወደ ማደሪያኸ ይግባ። እንወድሃለን ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር እናመልክሃለን!!
የሕመሞች ሁሉ መድኃኒት የኾነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፈውስ ይኹነን አሜን፡፡
ዲያቆን ሸዋፈራው
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

ይቆየን

እውነት ለሁሉ

14 Nov, 07:54


🥀#Na_ilaali_maalo🥀

Na ilaali maalo anoo nama hin qabu
Of biraatin dhabee namaa ol na qabu
Beekumsiif humnikoo si'idha abdin koo
Na bira hin darbinii na fayis uumakoo
🥀
#Ceesisa
🥀
Beela'ee dheebodhe yoon bules hagabuu
Marromaan koo maree yemmuuttin gaggabuu
Nama si waamatee si'i kan qaaqabu
Maalo naa gargaari anoo nama hin qabu
🥀
#Ceesisa
🥀
Jaamadha naan jedhee hundumtu na gatee
Anis naman dhabe namnis natt hammaate
Boolla dukkanatti gadi na daarbatu
Si qofadhaa gofta kan na fayyifatuu
🥀
#Ceesisa
🥀
Si barbaachun dhufe mana kooti ka'e
Si arguun barbaade mukaattan olba'ee
Na dura gorani na dhoksun fuula kee
Anoo nama hin qabu na fayis ilma kee
🥀
#Ceesisa
🥀
Nama of biraa dhabee yoon dhabees fayinaa
Fayyuu osoon barbaadu ciisee bishaan cinaa
Dhukubsadhee ciisee waggoota hedduu kanaa
Fayyii galii jettee deemi garaa mana

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊያን እንዲደርስ
👉
#share እና #join ያድርጉ ያስደርጉ
👉
@enatachinmaryam

እውነት ለሁሉ

14 Nov, 07:54


https://www.youtube.com/watch?v=4Ks1bvvMoKM

እውነት ለሁሉ

14 Nov, 07:54


🛑Na Ilaali Maloo,F/taa Biqilaa Mitikkuu,Faarfannaa Afaan Oromoo Ortodoksii Tewahidoo haaraa ,2022

ለሁሉም ኦርቶዶክሳዊያን እንዲደርስ
👉
#share እና #join ያድርጉ ያስደርጉ
👉
@enatachinmaryam

እውነት ለሁሉ

13 Nov, 18:47


“ የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል ” ዮሐ 1፥46
ክርስትና የሕይወት ኹሉ መሰረት የቤተክርስቲያን ራስ እና መዓዘን የኾነውን ጌታ ክርስቶስ ኢየሱስን ማግኘት ነው ፤ መራራዋ ሕይወት ጣዕም የሚኖራት ፣ ጨለማው ኑሯችን በብርሃን የሚሞላው ፣ ደካማ የኾነው ማንነታችን ብርቱ የሚኾነው ፣ ጸዳልና አብርኾት ተላብሰን በጽድቅ የምንመላለሰው ኢየሱስን ስናገኘው ነው ። የቤተ ሳይዳው ፊልጶስ  በሙሴ ሕግና በነቢያት ትንቢት የተነገረለት ምሳሌ የተመሰለለት ሕዝቡን ኹሉ ከጨለማ ፣ ከኃጢአት ፣ ከበሽታ ፣ ከደዌ ፣ ከዘለዓለማዊ ሞት ፣ ከሐዘንና ከጭንቀት ነጻ አውጥቶ በነጻነት እንዲመላለስ የሚያደርገው መሲሁ ናዝራዊ ኢየሱስን ባገኘው ጊዜ ለናትናኤል "የናዝሬቱ ኢየሱስን አግኝተነዋል" አለው ።

"ኢየሱስን ማግኘት " በዘመኑ ብዙ ትርጉም ያለው ነው ። በዛ በኃጢአት ፣ በደዌ ፣ በጨለማ ፣ ተስፋ መቁረጥ ፣ በዲያብሎስ አገዛዝ ዘመን ፤ ጽድቅ ፣ መድኃኒት ፣ ብርሃን ፣ ተስፋ ቤዛ የኾነውን አዳኝ ጌታ ኢየሱስን ማግኘት ትልቅ ደስታ ፣ ፍስሐ ፣ ፈንጠዚያና ሰላምን የሚሰጥ ድንቅ ተአምር ነው ። ይሄ ጌታ 5500 ዘመን ተጠብቆ ፣ ተስፋ ተደርጎ የተገኘ(የተገለጠ) ነው ።ይሄ መሲህ የአዳም ተስፋ ፣ የሰው ዘር ኹሉ ናፍቆት የነቢያት ትንቢት የከበረው በግ ሕዝቡን ኹሉ ሊዋጅ የታመነ ሊቀ ካሕናት ነው ።

ናትናኤል "የናዝሬቱ (ናዝራዊው)" የሚለውን የፊልጶስን ቃል ሲሰማ በወቅቱ የነበረውን የናዝሬት ነዋሪዎች ኃጢአተኝነት በደለኝነት ታውሶት "ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን?" ዮሐ1:47 ሲል ጠየቀ ። ናትናኤል ያልተረዳው መልካም ነገር ከራቃት የኃጢአተኞች መዲና ከኾነችው ናዝሬት የመልካም ነገር ምንጭ መልካሙ እረኛ(ዮሐ 10፡11) ኢየሱስ መውጣቱን ነው ።ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ልዮ ከሚያደርጉት ምክንያቶች አንዱ ፍጹም እንደኛ ሰው ኾኖ የተገለጠው ከኃጢአት በቀር መኾኑ ነው (ዕብ 4፡15) እርሱን በኃጢአት የሚከሰው አንዳች አልነበረም (ዮሐ 8፡46) ይልቁንስ ሰዎች እስኪደነቁ እስኪገረሙ በሥጋዌው ወራት ኃጢአትን ሲያስተሰርይ (ሉቃ 7፡41) ሲምርና ይቅር ሲል ኃላም በመስቀል ላይ ለዓለሙ ኹሉ ኃጢአት እርቃኑን ተሰቅሎ ታርቆ ሲያስታርቀን ታይቷል(ዮሐ1፡29 ፣ ዕብ 2፡17)።

ናትናኤል ከሩቅ ኾኖ የኢየሱስን መልካምነት (ከናዝሬት አንጻር) ከሚጠራጠር ይልቅ ፊልጶስ "መጥተኽ እይ" አለው ።የጌታ ኢየሱስን መልካምነት የቀመሰ ቸርነቱ የተደረገችለት ፈጽሞ እርሱን ሊጠራጠር በርሱም ላይ ቃል ሊያወጣ አይችልም። በሕይወታችን ውስጥ ያገኘነው ያመነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ መልካም ነገሮችን አድርጎልናል ፣ በሥጋዊና በመንፈሳዊ በረከቶች ባርኮናል ፤ መከራ ውስጥ ሳለን ከመከራ ነጥቆ አውጥቶናል ፤ ከበሽታ ከደዌያችን ፈውሶ አቁሞናል ፣ ማጣታችንን በማግኘት ፣ ጭንቀታችንን በሰላም ፣ትዳር ማጣታችንን በትዳር በረከት ፣ ልጅ ማጣታችንን በልጆች በረከት ሞልቶታል ፤ ድካማችንን በእረፍት ሞልቶታል እርሱ ያላደረገልን መልካም ነገር የለም።

ምናልባት አንዳንድ ችግሮችና ምድራዊ መከራዎች ሲያጋጥሙን ቸርነትና ምሕረቱን ፣ መልካምነቱንና ለጋሽነቱን ዘንግተነው ይኾናል።በፈተና ውስጥ ሳለን ራሱ እንደኛ የተፈተነውን ኢየሱስን እንመልከት እርሱ ሊራራልን የሚችል ሊከ ካሕናት ወዳጃችን ነው ፤ ምሥጢራችንን ፣ ጭንቀታችንን ፣ መከራችንን ፣ ፈተናና ስቃያችንን በጸሎት ፣ በእንባ ከምስጋና ጋር እንንገረው ፤ በርሱ ተስፋ እናድርግ በእርሱም እንደገፍ ፣ ኢዮብን ከመከራ እንዳወጣው እናስብ ፣ 12 ዓመት ያለማቋረጥ ደም ሲፈሳት የነበረችውን ሴት ደሟ ቀጥ ብሎ እንዲቆም ያደረገው የናዝሬቱ ኢየሱስ የልብሱ ጫፍ እኮ ነው ! 38 ዓመት በአልጋ ቁራኛ በደዌ ዳኛ ተይዞ የነበረውን መጻዕጉን አልጋውን ተሸክሞ እንዲነሳ ያደረገው የናዝሬቱ ኢየሱስ ቃል እኮ ነው ! ሙታንን ያስነሳ ፣ ጎባጣን ያቀና ፣ ዕውራንን ያበራ ፣ ሽባን የተረተረ .....ድውያነ ሥጋን በተአምራት ድውያነ ነፍስን በትምሕርት የፈወሰ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነው!!!!

ይሄንን አምላክ እንደ ናትናኤል ቀርበን እንየው እንደ ፊልጶስ እንከተለው በርሱ እንመን በእርሱም እንተማመን።በየትኛውም ኃጢአት ውስጥ ብንኾን አይኹድ ስትዘሙት አግኝተናታል እንደ ሙሴ ሕግ ልንወግራት ይገባል ቢሉት "ኃጢአት የሌለበት ይውገራት " (ዮሐ 8፡10)በሚል ከሳሾቿን ያሳፈረው ጌታ የኛም ጌታ መኾኑን እናስብ ።ከሳሽ ዲያብሎስን አሳፍሮ በደሙ ሊያነጻን በሥጋው ሊቀድሰን የሚችል ብርቱ ጌታ ነውና በርሱ እንተማመን !!!

የናዝሬቱ ኢየሱስን እንደ ፊልጶስ ስናየው እንደ ናትናኤል እስካኹን ካየነው በላይ እናያለን(ዮሐ1፡51) ካገኘነው በረከት በላይ እንባረካለን ።የሕይወት ውሃ የኾነው ኢየሱስ በሥጋም በነፍስም እርካታ ይኾንልናል ። ኢየሱስን የምናገኘው በቤተክርስቲያን ውስጥ ፣ በተቀደሰችው ጉባኤ ፣ በሰማይና በምድር ባለች በቅዱሳን ሕብረት ውስጥ ስለኾነ ዘወትር በአምልኮቷ እየተገኘን ፣ ቅዱስ ቁርባንን እየተቀበልን ፣ በቃሉ እየተሞላን ኢየሱስን እናግኘው !!!

ጌታ መንፈስ ቅዱስ ኢየሱስን እንድናገኘው ፤ ከምናምንቴዋ ዓለም ተለይተን እርሱን እንድንናፍቅ በከበረው ሰረገላ እንድንኖር ይርዳን አሜን!!
ኢየሱስን ያላገኙ ማግኘት ይኹንላቸው....!
ምሥጋና ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ አሜን!!
ዲያቆን ሸዋፈራው
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

ይቆየን

እውነት ለሁሉ

12 Nov, 19:47


የሙስሊም ጴንጤዎች በሉአቸው እነዚን 😁😁🙈

መስኪድ ውስጥ ጭፈራው ሌላ ታሪክ 😁😁

እውነት ለሁሉ

12 Nov, 15:46


"በሥጋ ያዩት ሰቅለውታል በመንፈስ ያዩት ሰግደው ፣ጌትነቱን መስክረው ፣ አምልከው ድነውበታል"
" የእግዚአብሔር ልጅ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ኾይ እኔ ኃጢአተኛውን ማረኝ አሜን! 🥰"

………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

12 Nov, 12:30


https://vm.tiktok.com/ZMhpeKqYs/


እሄ አካውንት ሼር ኮፒ ሊንክ አርጉ እስልምና ሸሆች ፍትሀዊ ያለሆነ ወሬአቸውን እያወሩ ነው

እስኪ እንደው በልበ ቀና ምትከታተሉ አይናችሁ ያልታወረ ሙስሊሞች ምን አረገ ልጁ 🤔
በማስረጃ ነው ሚያወራው ለውይይትምኳ ወሂድ ከእፎይ ጋ ለመወያየት ፍቃደኛ አደለም እስልምናው ነው በራሱ ተፍሲር የማናምነውን እየነዛ ሚሳደበው


ነፍስ ማጥፋት ማሳሰር ጀግና አያስብልም ጀግንነት በነፍሱ ወስኖ ሚያወራው ነው ጀግና ሚባለው

ከጎኑ ልንሆን ይገባል በተለይ ምታቁትም በአካባቢው

ብቻ አበረታቱት በተለይ ሀቀኛም እውነተኛ የሆናችሁ ሙስሊሞች ከእፎይ ጎን ልቆሙ ነው ሚገባው

እውነት ለሁሉ

12 Nov, 10:30


የቅዱሳን አማላጅነት ለምን አስፈለገን ?!!

በዲያቆን ሔኖክ ሀይሌ ❤️❤️❤️🙏

እውነት ለሁሉ

12 Nov, 06:59


ኡኡኡኡ ኧረ ተዘረፍን አላህ ሰረቀን 😂

ማስረጃው ያውና 👇

“ዳግመኛም እላችኋለሁ፥ ባለጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢገባ ይቀላል አለ።”
  — ማቴዎስ 19፥24

إِنَّ الَّذِينَ كَذَّبُوا بِآيَاتِنَا وَاسْتَكْبَرُوا عَنْهَا لَا تُفَتَّحُ لَهُمْ أَبْوَابُ السَّمَاءِ وَلَا يَدْخُلُونَ الْجَنَّةَ حَتَّىٰ يَلِجَ الْجَمَلُ فِي سَمِّ الْخِيَاطِ ۚ وَكَذَٰلِكَ نَجْزِي الْمُجْرِمِينَ

እነዚያ አንቀጾቻችንን ያስተባበሉ ከእርሷም የኮሩ ለእነርሱ የሰማይ ደጃፎች አይከፈቱላቸውም፡፡ ግመል በመርፌ ቀዳዳ እስከሚገባም ድረስ ገነትን አይገቡም፡፡ እንደዚሁም አጋሪዎችን እንቀጣለን፡፡
7:40

እውነት ለሁሉ

11 Nov, 18:39


በምታወሩበት ርእስ ምልጃ ነው ከፍ በላችሁ ይጠቅማችኃል የተቀረውን ሌላ ጽሁፍ ፈልጋችሁ አንብቡት በምዕራፍ የተከፈለ ስለሆነ

እውነት ለሁሉ

11 Nov, 18:38


የቅዱሳን ምልጃ ለምን አስፈለገ ክፍል ሶስትየቅዱሳን አማላጅ ለምን አስፈለገ እራሱ በቅዱሳን ምልጃ ስለሚፈልግ በመፅሀፍ እግዚአብሔር የቅዱሳንን አማላጅነት እንደሚፈልግ ተናግሯል እንዴት ቢባል እሄን ማሳያ አራት ነገሮችን እንመለከታለን በምልጃ ግዜ ሁሌም ሶስት ወገን አሉ እንደሚታወቁ ተማላጁ አማላጁ እና የሚማለድለት አስማላጁ አለ። ተማላጁ እግዚአብሔር ነዉ ከእርሱ ከእግዚአብሔር ዉጭ የሚማለድለት እና የሚያማልድ ሁለት ወገኖች አሉ በእኛ ቋንቋ ሀጥአንን እና ጻድቃን ከእግዚአብሔር ዉጭ ያሉ ሀጢያተኞች እና ጻድቃን በምልጃ ሂደት ዉስጥ እንዲተጉ እግዚአብሔር ሲገፋፋ እናያለን
አንደኛዉ ምንድነዉ እግዚአብሔር ወደጻድቃኑ ሂዳችሁ አማልደኝ በሉ ብሎ እግዚአብሔር እራሱ ሲልክ እናያለን
📖ዘፍ20÷7አሁንም የሰውዮውን ሚስት መልስ ነቢይ ነውና፥"ስለ አንተም" "ይጸልያል"፥ትድናለህም።
አባታችን አብርሀም ጌራራ ወደተባለች ሀገር ሄዶ ነበርና የነገሰዉ ንጉስ አቤሜሌክ ይባላል ሚስቱን እንዳይቀማ ስለፈራ ሚሱቱን ሳራ እህቴ ናት ብሏል ይሄን ግዜ አቤሜሌክ ሳራን ለማግባት ወስኖ እያፋጠነ በሌሊት እንዳትነካት የነብይ ሚስት ናት ብሎ እራሱ እግዚአብሔር አስጠነቀቀዉ ሳናዉቅ ሀጢያት ዉስጥ እንድንገባ አያደርግም  ይህ ሰዉ እኔ አላወኩም አለ ስላላወክ ነዉ ምነግርህ አለዉ እግዚአብሔር ስለዚህ አሁንም ሚስቱን መልስለት አለዉ እሱ ነብይ ነዉ ወደ እሱ ሂድ እሱ ስላንተ ይፀልያል እኔም ይቅር እልሀለዉ አለዉ እግዚአብሔር የጌራራዉን ንጉስ አቤሜሌክን ይፀልይልህ ብሎ ሚልከዉ ወደ አብርሀም ነዉ ሀጢያተኞችን ወደ ፃድቃን ሂዱ እና አማለደኝ በሉ ይላል እገዚአብሔር እንግዲህ አቤሌክ ቀጥታ እያናገረ ያለዉ እግዚአብሔርን ነዉ በል ለምነኝ ይቅር ልበልህ አላለዉም ሂድ እና ለአብርሀም ንገረዉ አብርሀም ደሞ ወደ እኔ ይፀልይ እኔ ደሞ ይቅር እልሀለዉ ነዉ ያለዉ ሁለተኛዉ,መፅ ኢዮብ 42÷8 ኺዱ፥የሚቃጠልንም መሥዋዕት ስለ ራሳችሁ አሳርጉ ባሪያዬም "ኢዮብ ስለ" "እናንተ "ይጸልያል"
ፃድቁ እዮብ እንደምናቀዉ በመከራ የኖረ እና የተገሰ ፃድቅ ሰዉ ነዉ ይህ ሰዉ በደዌ ተመቶ በሚሰቃይበት ሰአት ጓደኞቹ መጥተዉ በማፅናናት ፈንታ በቁስሉ ላይ ጥዝጣዜ ይጨምሩበት ነበር ከእሱም አልፈዉ በእግዚአብሔር ላይ የድፍረት ንግግር ይናገሩ ስለነበር እግዚአብሔር አዝኖባቸዉ ስለ ነበር ሶስቱን የኢዮብ ጓደኞች በታሪኩ ፌ
ፍፃሜ ላይ መፅሀፈ ኢዮብ ምዕ42ላይ ከሶስቱ ጓደኞች አንዱን ቴማናዊውን ኤልፋዝን እንዲህ ሲል ተናገረዉ እንደ ባሪያዬ ኢዮብ ስለኔ መልካም ነገርን አልተናገራችሁምና ቁጣዬ ባንተና በሁለት ጓደኞችህ ላይ ነዷል ስለዚህ አሁንም ወደ ባሪያዬ ወደ ኢዮብ ሂዱ.. ልብ በሉ እንግዲህ ወይፈን ይዛችሁ መስዋእት አዘጋጅታችሁ ወደ ኢዮብ ሂዱ ኢዮብ ስለእናተ ይፀልያል እኔም ፊቱን ወይም ፀሎቱን እቀበላለዉ እዚህም ጋ እንደምናየዉ ላኪዉ እግዚአብሔር ነዉ ሀጢያተኞችን ወደ ፃድቃን ሂዳችሁ ለምኑልኝ በሉ ይላል እሄ ደሞ ምልጃ ዙሪያ ጥምጥም ለሚመስለዉ ለሚመስለዉ ሰዉ እራሱ እግዚአብሔር ሲያረገዉ ነዉ ያየነዉ እግዚአብሔር ወደ ፃድቁ እገሌ ሂደህ እሱ ላንተ ይለምንልህ እኔ ይቅር እልሀለዉ ሲል እናያለን

ሁለተኛዉ ደሞ ፃድቃንን ወደ ምልጃ ሲገፋፋ እናያለን እሄን ደሞ ዘጸ32÷32 ላይ እናያለን እስራኤላዉያን ከግብፅባርነት ከወጡ በሀላ ጥጃ ሰርተዉ ከግብፅ ባርነት ነፃ ያወጣን ብለዉ ለጣኦት ሰግደዉ ነበር እግዚአብሔር ሙሴን እንዲህ አለዉ ከግብፅ ምድር ያወጣህዉ ህዝብህ በድለዋል አለ አንገተ ደንዳና ናቸዉ ማለትም ያረኩላቸዉን ዞር ብለዉ የማያስቡ ናቸዉ እና እንዳጠፋቸዉ "ተወኝ" በእዉነትእግዚአብሔር ከፈለገ ማጥፋት ከፈለገ ለምን ተወኝ አለ ዘፀ18÷17 ላይ እኔ የማደርገዉን ለአብርሀም እሰዉራለዉ ለአብርሀም ሳልናገር እሰራለዉ ይላል ማጥፋት ከፈለገ ቅዱሳኑን ሳይናገር ማጥፋት ይችላል እንደዉም ሙሴን ሲፈትነዉ አተን ታላቅ ሕዝብ አደርግሀለዉ ግን ተወኝ አለዉ ተወኝ ሚያስብለዉ እግዚአቤሔር ማን ሚከለክለዉ አለ አጠፋቸዉ ዘንድ ተወኝ ለምን አለ ማጥፋት ፈልጓል እግዚአብሔር ለምን ለሙሴ መንገር አስፈለገ አታጥፋ ሲሉትም እነሱን ጨምሮ ማጥፋት ይችላል እግዚአብሔር ግን ለሙሴ የነገረዉ ሙሴ ምን እንዲል ነዉ ሙሴ ስለሕዝቡ እንዲፀልይ ነዉ ዘፀ 32÷32 ላይ ሙሴ ስለ ሕዝቡ የፀለየዉ እግዚአብሔር  ቅዱሳኑን አማላጅነት ስለሚፈልግ ነዉ ዳዊት ሲናገር የሙሴን ምልጃ
📖እንዳያጠፋቸው ቍጣውን ይመልስ ዘንድ የተመረጠው ሙሴ በመቅሠፍት ጊዜ በፊቱ ባይቆም ኖሮ፥ያጠፋቸው ዘንድ ተናገረ። መዝ105÷23
እናም እግዚአብሔር ሕዝቡን ማጥፋት ሲፈልግ ለቅዱሳኑ ይናገራል የሚናገረዉ ለመረጃ ያክል አደለም እደዛ ከሆነ ካጠፋ በሀላ መናገር ይችላል ለቅዱሳኑም ሳይናገር የሚሰራ አምላክ ነዉ  ግን ቅዱሳንን ወደ ምልጃ ሲገፋፋ ነዉ ።
ፃድቃን ወደ እኛ ካላማለዱ ሀጥያት አርጎ ይይዜባቸዋል  እስራኤላዉያን ነቤዩ ሳሙኤልን ባስቀየሙ ሰአት ፀልይልን አሉት ነብዩ ሳሙኤልም ምን አለ..
📖ደግሞ መልካሙንና ቅኑን መንገድ አስተምራችኋለሁ እንጂ ስለ "እናንተ መጸለይን" በመተው እግዚአብሔርን" እበድል ዘንድ ይህ ከእኔ ይራቅ። 1ሳሙ 12÷23  ስለዚህ አንድ ፃድቅ ባያማልድ ፃድቅ ሁኖ እግዚአብሔርን እየበደለ ነዉ ያለዉ ማለት ነዉ ኢሳ59÷16 እግዚአቤሔር ፌርድ ስለሌለ አየ ተደነቀ ወደ እርሱ የሚማልድ እንደሌለ ተረዳ ይላል እንኳን አማላጅ ሊከለክል አማላጅ ሲጠፋ ለራሱ ይደንቀዋል በመፅሀፉ መሠረት እና የቅዱሳን አማላጅነት እግዚአብሔር ይፈልገዋል ሀጢያት አርጎ ይቆጥርባቸዋል ካማለዱም ደሞ ሚጠቀሙት ራሳቸዉ ናቸዉ የቤተ ክርስቲያን እራስ ክርስቶስ ነዉ ልብ አርጉ እኛ የአካሉ ብልቶች ነን ቅዱስጳዉሎስ 1ቆሮ 12÷12-27 እኛ የአካሉ ብልቶች ነን አንዱ አካል ደሞ ለአንዱ አካል ጤንነት ይጨነቃል እንደዉም የከበሩ የማይመስሉንን አካላት በይበልጥ እንከባከባቸዋለን ለቤተክርስቲያን እኛም ፃድቃንም ብልቶቿ አካሎቿ ነን እኛ ህመምተኛዉ አካል ነን ህመምተኛዉ አካል ሲሰቃይ እኔ አይመለከተኝም እንደማይል ሁሉ ፃድቃንም ደሞ ስለ ሀጢያተኛዉ ከነሱ ስለማይለየዉ አካል ስለደከመዉ ከእነሱም ስለሚያንሰዉ ሰዉ ይፀልያሉ ይህን የሚያደርጉትም ለራሳቸዉም ጭምር ነዉ ፍቅር ከሌላቸዉ ከንቱ ስለሚሆኑ እራሳቸዉም ይጠቀማሉ ቅዱሳን በማማለዳቸዉ በመፅ ኢዮ ላይ ኢዮብ ፀለየላቸዉ ለባልእንጀሮቹ ምርኮዉም ተመለሰለት እንደዉም እጥፍ ሁኖ ይላል ኢዮ49÷10 በመፅሀፍ መሠረት አንድ ፃድቃን ለእኛ በመፀለዮ እሱ እኛን ይጠቅማል ብቻ ሳይሆን እነሱም ይጠቀማሉ አባቶች ፀሎትን በቅባት ይመስሉታል አንድን ሰዉ ሰዉን ቅባት ቢቀባ እራሱም መቀባቱ እጁ አይቀርም  እናም ፃድቃን ወደ እኛ ባለመፀለያቸዉ እግዚአብሔር ይኮንናቸዋል እነሱ ብቻ ፀድቀዉ  እኛ ተኮንነን እንድንቀር አይፈልግም አካል ነን ከተባለ እንደዛዉ ነዉ ጳዉሎስ ራሱ ክርስቶስ እና እኛን አካሎቹን በሰዉ ሰዉነት ክፍሎች አርጎ አስተምህሯል አንድ ሰዉ ሲወፍር ነዉ ተስማማዉ የሚባለዉ አንድ ሰዉ ከወፈረ ተስማማዉ አደገ ይባላል እጁ "ብቻ" ወፈረ ቢባልስ አበጠ በሽታ ነዉ ሚባለዉ በቅዱሳንም እነሱ ብቻ ቅድስና ኑሮ እኛ ወድቀን እንድንቀር አይፈልጉም የመፅሀፍ ቅዱስ አስተምህሮ ነዉ ጳዉሎስ እንዳለዉ

እውነት ለሁሉ

11 Nov, 14:28


ጀምራ፣ ስብሐት ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በማለት ስሙን እየጠራችና እያመሰገነች ተግባሯን ትፈጽማለች፡፡

ታውቃላችሁ፣ ማንም ሰበከው ማንም የክርስቶስ ስም ሲሰበክ ስሙ ኃይል አለውና – ደስ ይለናል ! ከብዙ ቅንአትና ክርክር ልማድና ወጎች መሀል፣ ከብዙ ፍልስፍናዊ ቅዠቶችና መላምቶች መሀል፣ ከብዙ ፖለቲካዊ ዲስኩሮችና ፕሮፓጋንዳዎች መሀል፣ ጥቂት የተነገረ የክርስቶስ ስም ኃይል አለውና ነገር ግን ስሙን ለኑፋቄ እንዲሁም ለተቃውሞ ስጠሩት እንቃወማለን – በዚህ ደስ ይለናል!
ዲያቆን ሸዋፈራው (Orthodox and Bible)
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

11 Nov, 14:28


‹‹ክርስቶስ ይሰበካል ስለዚህም ደስ ብሎኛል››ፊልጵ 1፡18
“ … አንዳንዶች ከቅንአትና ከክርክር እንኳ ሌሎች ግን ከበጎ ፈቃድ የተነሣ ክርስቶስን ይሰብኩታል፤ እነዚህ ወንጌልን መመከቻ ለማድረግ እንደ ተሾምሁ አውቀው በፍቅር ይሰብካሉ ፥ እነዚያ ግን በእስራቴ ላይ መከራን ሊያመጡብኝ መስሎአቸው ፥ ለወገናቸው የሚጠቅም ፈልገው በቅን አሳብ ሳይሆኑ ስለ ክርስቶስ ያወራሉ። ምን አለ? ቢሆንም በሁሉ ጎዳና፥ በማመካኘት ቢሆን ወይም በቅንነት ቢሆን፥ ክርስቶስ ይሰበካል ስለዚህም ደስ ብሎኛል።” (ፊልጵ.1፥15-18)
ወገኖች ሆይ፣ ክርስትና ክርስቶስን መምሰል፣ የክርስቶስን ሕይወት መስበክ ነው፡፡ ክርስቶስን መስበክ ስንል ደግሞ ከድንግል እናቱ ከእመቤታችን ቅድስት ማርያም ሥጋ ነስቶ መወለዱን፣ በምድር ላይ የእግዚአብሔርን መንግሥት በቃልና በሥራ መስበኩን፣ በመስቀል ላይ ስለኃጢአተኞች መሞቱን፣ መቀበሩን፣ በክብር ከሞት መነሳቱንና ወደ አባቱ ማረጉን፣ በመጨረሻውም ቀን በሕያዋንና በሙታን ሊፈርድ ዳግም ምጽአቱን ብቸኛ /ከባህሪ አባቱ ከአብ ከባህሪ ህይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር/ የባህሪ አዳንነቱን ጌትነቱ እና አዳኝነቱን … ለሰዎች መናገር ነው፡ ወገኖች ሆይ፣ አንዳንዶች ስለ ክርስቶስ ሲናገሩ ወይም ሲያወሩ የምንሰማው ከቅንአትና ከክርክር መንፈስ ተነስተው ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ለራሳቸው ዓላማ፣ ለገዛ ራሳቸው ሀሳብ እና ጥቅም ሲሉ፣ በቅን አሳብ ሳይሆን ቅንነት በጎደለው መንገድ ስለ ክርስቶስ ያወራሉ። እነዚህ ሰዎች በእውነተኛ የክርስቶስ መስካሪዎችና ተከታዮች ላይ መከራ ለማምጣት ስለ ክርስቶስ ያወራሉ። ስለክርስቶስ ያላቸው ንግግር ሁሉ ወሬ ነው ፡፡በተለይም ቅዱሳኑን ለማናናቅ እና ለማጥላላት ለክርስቶስ ቀናኢ መስለው ስለ እርሱ ያወራሉ እነዚህ ሰዎች ስብከታቸው ፅሁፋቸው ሁሉ በእልህ ስለሆነ ወሬ ነው ! ኢየሱስ የሚሰበከው በጸጋ እና በእውነት እንጂ በእልህ እና በፉከራ ሽለላ አይደለም ፡፡እኛ ከምንም በላይ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ክርስቶስን በመስበካቸው /ወሬ ካልሆነ ማለት ነው/ እንደሰታለን ፤ ቅዱሳንን በመንቀፋቸው ደግሞ እንቃወማቸዋለን ፡፡በአንዳችም ምክንያት ኢየሱስ ተሰበከ ብለን ቅር አንሰኝም ይልቁንም እንደሰታለን እንጂ !! ስለክርስቶስ ሲያወሩ ቅንነት ጎደላቸው ራሳቸውን አሳበዩ እንጂ ስሙን አታንሱ ስሙን አትጥሩ ያላቸው ከኛ ወገን ማንም የለም !! ስለክርስቶስ የሚያወሩት ግን ቤተክርስቲያንን ለማጥላላት እንደማታውቀው ለማስመሰል እንጂ ስሙ ገዷቸው አይደለም !!እነዚህ ሰዎች ራሳቸውን የክርስቶስ ሰባኪ አስመስለው ሌላውን አካል ደግሞ የስሙ ነቃፊ እያደረጉ ይስላሉ !!ጥቂት እምነት ከጥቂት እውቀት ያለን ሰዎች/እውቀታዊ ሆነ እመነት እንጂ የጸጋው እምነት እንዳላልኩ ልብይሏል / ከባድ ድንቁርና አለብን... ያልተገባንን ዕውቀት አለን ብለን የምናወራ ... ሙሉ ቁና ሰፌድ የሚያክል ኩራት ተሸክመን እስከመቼ???? ራሳችንንስ አሳብየን እስከመቼ እንዘልቃለን????
ወገኖች ሆይ፣ አንዳንዶች ደግሞ፣ ከቅን አሳብ እና ከፍቅር ተነስተው ክርስቶስን ይሰብካሉ፡፡ እነዚህ ወገኖች ታላቁ ተልዕኮ አምነው ተቀብለው፣ የሰው ልጆች ሁሉ እውነቱን እንዲያውቁ፣ ድኅነት እንዲያገኙ ወንጌል ይሰብካሉ፡፡ በዚህም ብዙዎች አማኞች ይሆናሉ፡፡
እኛስ ዘወትር ኢየሱስን ከነገሮች ሁሉ በላይ ከፍ አድርገን በልባችን አንግሰን እንዲህ እያልን እንሰብከዋለን የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ኃያልና ከስም ሁለ በላይ የሆነ ስሙን እየጠራን ከባሕርይ አባቱ ከአብና ከባሕርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ያለውን ዕሪና (ትክክልነት) ሳናጓድል እንሰብከዋለን፡፡ ስለዚህም በእንተ ማርያም እሙ፣ በአማኑኤል ስሙ ብሎ ይማረን፡ በማለት በጸሎት ወቅት ስሙን በመጥራት፣ “ንሰግድ ለከ ክርስቶስ ምስለ አቡከ ኄር ሰማያዊ ወመንፈስከ ቅዱስ ማሕየዊ” “ክርስቶስ ለአንተ እንሰግድልሃለን ከሰማያዊ ከቸር አባትህ ጋር አዳኝ ከሆነ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር” በማለት ለአምላክነቱ የሚገባውን ስግደት በማቅረብ ስሙን እየጠራን እናከብረዋለን፡፡ “ዝ ውእቱ ጊዜ ባርኮት፤ ወዝ ውእቱ ጊዜ ዕጣን ኅሩይ፡፡ ጊዜ ሰብሖቱ ለመድኃኒነ መፍቀሬ ሰብ ክርስቶስ” “የማመስገን ጊዜ ይህ ነው፤ የተመረጠ የዕጣን ጊዜም ይህ ነው፡፡ ሰውን ወዳጅ የሆነ መድኃኒታችን ክርስቶስን ማመስገኛም ጊዜ” በማለት ደግሞ የሚገባውን ውዳሴ ለምስጋና የሚሆን ጊዜ ሰጥተን እናቀርባለን፡፡

ቤተክርስቲያናችን ወንጌል የሚተርከውን የአብ አንድያ ልጅ መድኅን ክርስቶስ በመስበክ ረገድ አንዳች ህጸጽ የለባትም፡፡ፍጽምት ናት!!

(ሀ) 18 በዐላትን በጌታ ስም ሰይማ በተለየ ሁኔታ ታከብራለች፡፡9ኙ ማለትም፡ የመጋቢት 29ኙ ብስራት ወይም ትስብዕት፣ልደት፣ጥምቀት፣ደ/ታቦር፣ሆሳዕና፣ስቅለት፣ትንሣኤ፣ዕርገት እና ጰራቅሊጦስ በማንኛውም ቤ/ክ ውስጥ ከፍ ባለና አገራዊ ስሜት ባለው መልኩ ይከበራሉ፡፡የተወሰኑት እንደውም ብሔራዊ በዐላት ናቸው፡፡ከ9ኙ ንዑሳት የጌታ በዐላትም ማለትም ከመስቀል፣ስብከት፣ብርሃን፣ኖላዊ፣ግዝረት፣ልደተ ስምዖን(ጌታ በዘሌዋ 12 መሰረት በኦሪቱ ህግ በ40 ቀኑ ወደ መቅደስ ሲገባ ስምዖን በሉቃ 2 ቁ 29 ጀምሮ ያለውን የጸለየበት ቀን)፣ቃና ዘገሊላ፣ደ/ዘይት እና የመጋቢት መስቀል በተለየ መልኩ ከወንጌሉ ጋር ተሳስረው በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ይዘከራሉ፡፡የቅዱሳን በዐል ሲሆን ግን ቅዱሱ የሚዘከረው በስሙ በታነጸው ቤተክርስቲያን ብቻ ነው፡፡ለምሳሌ ሚያዚያ ጊዮርጊስ የሚዘከረው በቅ/ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ወይም ጽላቱ ባለበት ደብር ብቻ ነው፡፡ጥምቀት ግን የጌታ በዐል ስለሆነ በሁሉም ይከበራል፡፡ልደትም፣ትንሳኤም እንደዛው ነው፡፡በሁሉ ይከበራል፡፡ይሄ ደግሞ ፕሮቴስታንት/ተሐድሶ / ከመምጣቱ በፊት ድሮ በጣም ድሮ የተጀመረና አሁንም የቀጠለ ነው፡፡ስለዚህም ነው ክርስቶስን እናስተዋውቃችሁ ስትሉን የምንስቀው፡፡ቀድመን አምላክነቱን አውቀን አክብረነዋላ!!

(ለ) “ቁማችሁ አዳምጡ!” ሲል ዲያቆኑ አውጆ በካሕኑ የሚነበበውን ቃለ-ወንጌል ጨምሮ በቅዳሴው መሃል ብቻ 4 የመጽሐፍ ቅዱስ ምንባባት አሉ፡፡ማኅሌት ያለ እንደሆነ ደግሞ ከእስመለዓለም በፊት ወንጌል መነበቡ ግድ ነው፡፡ያውም በገጠሪቱ ኢትዮጵያ በተለይም በሰሜኑ የትርጓሜ-ሐዲስ መምር ከተገኘ እስመለዓለም ላይ የሚነበበው ወንጌል በአንድምታ ተተርጉሞ ይሰማል፡፡ለኦርቶዶክሳውያን ወንጌል ብርቃችን ሳይሆን ትጥቃችን ነው የምንል ለዚህ ነው፡፡

(ሐ)ቤተክርስቲያን ክርስቶስን እንደ ክርስቶስነቱ የማትጠራበት ጊዜም የለም፡፡ የስሙም ጣዕም ዘወትር ከአንደበቷ የማይጠፋ ነው፡፡ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ “ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ስም ለዘይጼውዖ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ቃል ለዘያጸምዖ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ሥጋ ለዘይበልዖ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ደም ለዘይሰትዮ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ፄና ለዘያፄንዎ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ጥዑመ ዝክር ለዘይነግር ዜናሁ ” “ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠራው ስሙ የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚያዳምጠው ቃሉ የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚበላው ሥጋው የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሚጠጣው ደሙ የጣፈጠ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ዜናውን ለሚነግር መታሰቢያው የጣፈጠ ነው ” ያለው መቼ በከንቱ ሆነና (መጽሐፈ ምሥጢር፣ የዕርገት ምንባብ):: ስለሆነም ቤተክርስቲያን ስመ ክርስቶስን ከመጥራት የምትከለከልበት/የምትከለክልበትም / ጊዜ የለም አይኖርምም:: ሊኖርም አይችልም !!!!!!ከዚህ ባሻገር ማናቸውም ሥራ “በስመ አብ ወወልዴ ወመንፈስ ቅደስ አሐዱ አምላክ በማለት ስሙን በመጥራት

እውነት ለሁሉ

10 Nov, 13:06


እግዚአብሔር ፈጽሞ ሰው አይጥልም!

ትላንት አገልግሎት ጨርሼ ከዐውደ ምህረት ወርጄ ወደ ስብከተ ወንጌል ክፍል በማመራበት ጊዜ የአንዲት እህት ድምጽ ደጋግማ "መምህር መምህር...." ብላ ስትጠራኝ ሰምቼ ዘወር ብዬ አይቻት ጠበኳት ፡፡አጠገቤ ደርሳ ሰላምታ ሰጠችኝ እኔም ሰላምታውን ተቀብዬ ሰላምታ ሰጠኋትና " ምን ልርዳሽ የኔ እህት?" አልኳት እርሷም በሰጠሁት የወንጌል ትምህርት ተመስርታ " የበደልነውን የበደሉንን ይቅር ሳንል እግዚአብሔር ፆማችንን ጸሎታችንን ምጽዋታችንን እንደማይቀበል መፅሐፍ ቅዱስ ጠቅሰህ አስተምረሃል ጎረቤቶች ነበሩኝ ከሰራተኛዋ እና ከጎረቤቶቼ ጋር በሰራተኛዋ ምክንያት ተጣልቼ ነበር ፡፡ነገር ግን ፆም ከመግባቱ በፊት የታረቅን ሲሆን በሰራተኛዋ ላይ ቂም ባሊዝም ሰላም አልላትም ...... " አለችኝ ፡፡እኔም ለጥያቄዋ መፅሐፍ ቅዱሳዊ መልስ የሰጠኋት ቢሆንም ቀልቤን የገዛኝ የሁላችንም ጥያቄ የሆነው ሁለተኛው ጥያቄዋ ነው ፡፡ " እጸልያለው እፆማለው በቅዳሴው በሰዐታቱ ..... እገኛለው ነገር ግን የሥጋ ኑሮዬ መራራ ነው ትዳር የለኝም ትምህርት እምቢ ብሎኛል የረባ ገቢ የለኝም እግዚአብሔር ከእኔ ጋር የለም ማለት ነው እላለው አንተ ቃሉን መሰረት አድርገህ ስታስተምረን እኛ ወደ እርሱ ስንቀርብ እርሱም እንደሚቀርበን በበረከት እንደሚባርከን ነው ለእኔ ግን በተቃራኒው ነው የሆነው እገግዚአብሔር ጥሎኛል ....ያዕ4.:7-10" አለችኝ! በመቀጠልም " እህቶቼ በሃፍት በትዳር በልጆች ስለተባረኩ ቤተክርስቲያን የምትመላለሽው እግዚአብሔርን ደጅ የምትጠኝው ዝም ብለሽ ነው እኛ ሳንጸልይ ሳንፆም ደጅ ሳንጠና ባርኮናል እያሉ እምነቴን እየሸረሸሩት ነው......." አለችኝ፡፡ እኔም የእዮብን ታሪክ የሳሙኤልን እናት የሐናን እንባ እምነት የለሽ ባለሃፍቶችን ጠቅሼ በዝርዝር በቃሉ አጽናናኋት፡፡ደስ እያላት አመስግና ተሰናበተችኝ፡፡እግዚአብሔር በቃሉ ያጽናናል ያበረታል የወደቁትን ያነሳል "እግዚአብሔር ለእርሱ ሕዝብ ያደርጋችሁ ዘንድ ወድዶአልና እግዚአብሔር ስለ ታላቅ ስሙ ሕዝቡን አይተውም። "(1ሳሙ 12:22).በመከራችን ሰአት..እግዚአብሔር ዝም ያለ ሲመስል ፈጽሞ የማይረዳን ይመስለናል! ሲጀመር ችግር ችግር የሚሆንብን እኛ በአቅማችን በራሳችን ኃይል መወጣት የማንችለው ሲመስለን ነው! ሕይወት ሁልጊዜ ተራራ አይደለችም.. አንዳንድ ጊዜ በሸለቆ ማለፍ ይኖርብናል! በሸለቆ ውስጥ ስናልፍ ግን ማስተዋል የሚገባን..ከዚ በፊት እግዚአብሔር ያደረገልንን በጎ ነገር ማሰብ..የትላንቱን ማዕበል.. የትላንቱን ተራራ..የትላንቱን የችግር ቋጠሮ የፈታልን ጌታ አልሞተም ወይ አገር ጥሎ አልሄደም! ዛሬም ህያው ነው ክንዱ አልደከመም..! ቀን ከለሊት ፊቱን ለምትሻ ነፍስ ፊቱን አያዞርም! እግዚአብሔር ሰው አይደለም! ለበረታ ፊቱን ሰጥቶ ለደካማው ጀርባውን አያዞርም! ይልቅስ የምስኪኑ ወዳጅ..የተጣለውን ከአፈር ከትቢያ ከአመድ አንስቶ ለክብሩ የሚያቆም ጌታ ነው ጠላታችሁ..የሚፈታተናችሁ
.. የሚያንገላታችሁ..በዚም በዚያም የሚዋጋችሁ እግዚአብሔር አይደለም! ጠላታችሁ ቀናተኛው ሰይጣን ነው! ምስኪኖች ሆይ ጽኑ በእምነታችሁ! እግዚአብሔር ታማኝ ነው! ዛሬም ህያው ነው! ጠላት ምንም ቢያወራ..ምንም ቢያስፈራራ!!! አትፍሩ! እግዚአብሔር የማንም ሰው እንባ ባለ እዳ አይደለም! ቀን ጠብቆ የሁሉም ሰው እንባ ይታበሳል.
እግዚአብሔር ረሳኝ አትበሉ።
የፈጠረህ የፈጠረሽ፥ ከማኅፀን የተሸከመህ የተሸከመሽ እርሱ ነውና እግዚአብሔር ረሳኝ አትበሉ። ያልተፈጠረውን ቀናችሁን ያልኖራችሁበትን ወራት ያየ ነውና እርሱ ረስቶኛል አትበሉ። በእናታችን ማኅፀን ውስጥ የመገበን እርሱ ነውና ረስቶኛል አትበሉ።
ወደ ብርሃን ያመጣን፥ እስትንፋስን የሰጠን አልረሳንም፤ በእናታችን ጫንቃ ላይ ምቾት የሆነን አልረሳንም፤ ያቆመን አንደበት የሆነን አልረሳንም፤ ያሳደገን በበረከት የመረቀን አልረሳንም፤ ለምኞታችን ለክፋታችን ያልሰጠን አልረሳንም።
አልረሳንም፦ ፈጥሮ፣ መግቦ፣ አቁሞ፣ አሳድጎ፣ መክሮ፣ ሰው አድርጎ ለዚህች ቀን አድርሶናልና ረስቶናል አትበሉ።
ቀኑ ቢጨልምም አይረሳንም፤ በሐዘናችን ቀን እንኳ አይረሳንም፤ አቅጣጫ የጠፋን ሲመስለን አይረሳንም ፤ ለጥያቄዎቻችን መልስ ባይኖረን አይረሳንም።
« እናት የወለደችውን ልጅ ልትረሳ ትችል ይሆናል እኔ ግን አልረሳችሁም» ብሎአልናል።
« አልረሳህም ከቶም አልጥልህም» ብሎአል፡፡
ይረሳል አትበሉ እግዚአብሔር ሰው አይረሳም
ይጥላል አትበሉ እግዚአብሔር ሰው አይጥልም
ይታመናል ምሕረቱ ለዘልአለም
በመዳፉ ይዞታል ይሕን አለም
እግዚአብሔር ኢሳያስ 43:1-3 ለእስራኤሎች እንዲህ ብሎ አስታወሳቸው " አሁንም ያዕቆብ ሆይ፥ የፈጠረህ፥ እስራኤልም ሆይ፥ የሠራህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ተቤዥቼሃለሁና አትፍራ፤ በስምህም ጠርቼሃለሁ፥ አንተ የእኔ ነህ። በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፥ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥህም" ከዛሬ 2000 ዓም በፊት ደቀመዛሙርቶቹ ባህር እያቋረጡ እያለ ማዕበሉ አስጨነቃቸው ወዮ ጠፋን ብለው በፈሩበት ሰዓት ኢየሱስ በውሃ ላይ እየተረማመደ ቃል ኪዳኑን ጠበቀ " በውሃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ ወንዞቹም አያሰጥሙህም" ኢየሱስ እራሱን ለሙሴ ፣ ዘካሪያ ፣ለኢሳያስ እንደ ተናገው
ለጴጥሮስ ፣ዮሐንስ ፣... ለደቀመዛሙርቱ
" እኔ ነኝ፤ አትፍሩ አላቸው።" ማቴዎስ 10:24-27 አንቡት። ዛሬ በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ሁኚ ዛሬ በየትኛውም ቦታ ሁን ጌታ ኢየሱስ እንደዚህ ይልሻል " እኔ ነኝ አትፍሪ"
እንደዚህ ይልካል " እኔ ነኝ አትፍራ"
እግዚአብሔር ሰው አይጥልም!
ኢየሱስ ሰው አይጥልም!

………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

ይቆየን

እውነት ለሁሉ

09 Nov, 15:42


5 ቱም pdf ላይ የተጠየቁ ጥያቄዎች የተመለሱበት ነው

በዘፍጥረት ዘጸአት ዘሌዋውያን ዘኁልቁ እና ዘዳግም ላይ ለተጠየቁ ጥያቄዎች መልስ ሾፍ አርጎት ተወዳጆች ❤️❤️❤️🙏

እውነት ለሁሉ

09 Nov, 11:25


ፍትሐ ነገሥት ክፍል ፲፯ አንቀጽ ፳፫ ለክርስቲያኖች ስለሚገቡ ምግቦች፣ ልብሶች፣ ስለ ቤት እና ስለ ተግባረ እድ ይናገራል።
፩) በወንጌል የተከለከሉ ምግቦች ደም፣ ጥሬ ሥጋ፣ ታንቆ የሞተውን፣ ለጣዖት የተሠዋውን፣ የአውሬውን ትራፊ፣ ሙቶ የተገኘውን፣ ሲያርዱ አንገቱን ቆርጠው የጣሉትን ናቸው። ለጣዖት የተሠዋውን አትብሉ የተባለበት ምክንያት ምእመናን ወደ ጣዖት አምልኮ እንዳይሳቡ ነው።

፪) ርኵስ ፍጥረት እንደሌለ እግዚአብሔር የፈጠረው ፍጥረት ሁሉ ንጹሕ እንደሆነ ተጽፏል። መጽሐፍ ከከለከለው በቀር ከምግብ ሁሉ እንዳንከለከል መሆን ይገባናል።
_
፫) አእምሮ ወደማጥፋት የሚያደርስን ምግብ፣ አራቱን ባሕርያትን የሚያነዋውጽን ምግብ፣ አካል የሚያጎድልን ምግብ መብላት አይገባም። ይኽውም መርዝ እንዳላቸው እንስሳትና እፀዋት ያሉትን ነው።
_
፬) አትብሉት ከተባለው የምግብ ወገን ደህነኛውን የሚገድል ድውዩን የሚፈውስ ቢሆን ደህነኛው ከመብላት ይከልከል። ድውዩ ግን የሚያድነው ከመሆኑ የተነሣ መብላት ይገባዋል።
_
፭) ሁሉን ሊበሉት እንዲገባ የሚያምን ሰው ሁሉን ይብላ። የሚጠራጠር ሰው ግን እህል ይብላ። ሁሉን የሚበላ አረማዊም ሁሉን የማይበላ አይሁዳዊን ሃይማኖተ ግብዝ ብሎ አይንቀፈው። ሁሉን የማይበላ አይሁዳዊም ሁሉን የሚበላ አረማዊን ይህ ሁሉ በአፌ ብሎ አይንቀፈው።
_
፮) ለሰው ክፉ ነገር እየተጠራጠሩ መብላት ነው። በሃይማኖት የማይሠራው ሥራ ሁሉ ኃጢአት ነው። ለጣዖት የተሠዋውንኳ አምነው ቢበሉት ጉዳት አያመጣም።
_
፯) በመብል ምክንያት ወንድምህ የሚጎዳ ከሆነ የተፈቀደውን እንኳ ስለእርሱ ብለህ አትብላ።
_
፰) በገበያ የሚሸጠውን ሁሉ ብሉ። ፍጥረቱ ሁሉ የእግዚአብሔር ገንዘብ ነውና። እያመሰገኑ ቢቀበሉት ሁሉም በስመ እግዚአብሔር ይከብራል።
_
፱) ካላመኑ ሰዎች ወገን የጠራችሁ ሰው ቢኖር እና ልትሄዱ ብትወዱ ሳትመራመሩ ያቀረቡላችሁን ሁሉ ብሉ። ለጣዖት የተሠዋ ነው ቢላችሁ ግን አትብሉ።
_
፲) በቀለም ያስጌጧቸውን ልብሶች ከመልበስ መጽሐፍ ከለከለ። ቤተመቅደስ ገብተው እግዚአብሔርን ሲያገለግሉ የሚለብሱት ልብስ ነጭ ሊሆን ይገባል።
_
፲፩) ሴቶች የወንድ ልብስ አይልበሱ አለ። እጀ ሰፊ ቀሚስ፣ ሱሪ አይታጠቁ። አርዓያ መለወጥ ሥርዓት ማፍረስ ነውና። ወንዶችም የሴቶችን ልብስ አይልበሱ። ይኽውም እጀ ሰብስብ ቀሚስ አይልበሱ።
_
፲፪) ወንዶች ከጣታቸው ቀለበት አያግቡ የምንዝር ጌጥ ነውና። ሴቶች በወርቅ የተጌጠ የሚያስመካ ልብስ አይልበሱ። ሹማምንት ግን ያጌጠ ልብስ ቢለብሱ ይገባቸዋል።
_
፲፫) መነኮሳት ከፀምር ወገን ደጓሳ ልብስ ይልበሱ።
_
፲፬) ማንኛውም ሕዝብ የወደደውን መልበስ ይገባዋል። ዘመን ያስገኘውን መልበስ ዘመን ባስገኘው ማጌጥ ይገባቸዋል። ከሕዝባውያን ወገን ብዙዎቹ ሰዎች ያገኙትን መልበስ ይገባቸዋል።
_
፲፭) ካህናት የወታደር ልብስ አይልበሱ። ካህናት የአናፂ ልብስን አይልበሱ።
_
፲፮) ወጠቢብኒ ቅዱስ ባስልዮስ ይቤ ይደሉ ለነ ከመ ንሥራዕ ልብሰነ በዘንከድን ዕርቃነነ። ዕርቃናችንን እንሠውር ዘንድ ልብስ መሻት ይገባናል። ወንድኃን እምቍር ወዋዕይ። ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር ለመዳን ልብስ ያስፈልጋል [ቁጥር ፰፻፲፬]።
_
፲፯) ለሚኖሩበት ሰዎች ይጠቅም ዘንድ፣ ይሠውራቸው ዘንድ፣ ምግባቸውን ንብረታቸውን ያስቀምጡበት ዘንድ፣ ይሰበሰቡበት ዘንድ፣ ቤት መሥራት ይገባል።
_
፲፰) ጌታ ለወልደ እጓለ እመሕያውሰ አልቦቱ ኀበ ያሰምክ ርእሶ ተብሎ እንደተነገረው ቤት እንዳልነበረው ሁሉ ለባሕታውያንም በዚህ አብነት ቤት የላቸውም።
_
፲፱) የእንግዳ መቀበያ ይሆን ዘንድ ቤት ያስፈልጋል።
_
፳) ከሥራይ፣ ከጥንቆላ፣ ጣዖትን ከመሥራት፣ ከመዝፈን፣ ከተውኔት በስተቀር ክርስቲያን ሥራን ሁሉ መሥራት ይገባል።
_
፳፩) አንጥረኛ ሁሉ ጣዖት ከመሥራት ይከልከል። ከአመነ ከተጠመቀ በኋላ ይህን የሚያደርግ ቢኖር ንስሓ ይግባና ይተወው።
_
፳፪) ለጣዖት በገና የሚደረድር፣ የሚዘፍን ቢኖር በቀኖና ይለይ። ያም ባይሆን በውግዘት ይለዩ።
_
፳፫) ለክርስቲያኖች የሚገቡ ሥራዎች ግብርና፣ ማስገር፣ ልብስ መስፋት፣ ልብስ መሥራት፣ ቤት መሥራት፣ ሕክምና፣ አንጥረኝነት፣ ጠራቢነት፣ ጸሓፊነት፣ እንጀራ ጋጋሪነት ወጥ ሠሪነት፣ መምህርነት፣ ነጋዴነት፣ መርከብ መሥራት እና የመሳሰሉት ናቸው። ንግድ ከአንዱ ሀገር ያለውን ወደ አንዱ ሀገር ለመውሰድ በግድ ያለውድ ያሻል [ቁጥት ፰፻፳፬]።
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

08 Nov, 11:32


እስልምና...ያረጋል ሹፏት 😁

እውነት ለሁሉ

08 Nov, 11:24


"የክርስቶስ ቤዛነት ይህ ነው፦ እርሱ ስለተሸከማቸው ዘግናኝ ሕማሞች እና ኃጢኣቶች እስካሁን ድረስ ያለማቋረጥ ይናገራል። ኃጢኣት የማያውቀውን እርሱን እግዚአብሔር አብ ስለእኛ ሲል 'ኃጢኣት እንዲሆን' አደረገው። አመንዝራው፣ ስድ ሆኖ የሚበድለው፣ ቆሻሻ በሆኑ ተግባራት አረንቋ ውስጥ የሚዛቅጠው እና ኃፍረት አልባ በሆኑ ተግባራት የሚበላሸው ሁሉ ከክርስቶስ ሲሸሽ ድምጹ በኋላው ይከተለዋል። ይኸውም 'የተወደድህ ልጅ ሆይ፥ ና! ኃጢኣቶችህ ከእኔ ጋር ናቸው፤' እያለ የሚጣራ የእግዚአብሔር ልጅ ደም ነው! ገና የሠራሃቸው ዕለት ነው በምልዓት የተሸከምኳቸው። ካሣውን ከፍያለሁ፦ ሐፍረት ተጭኖብኛል፤ ተገርፌያለሁ፤ ደቅቄያለሁ፤ ተሰቅያለሁ፤ እንዲሁም መርገምን ተሸክሜያለሁ። ለአንተ የይቅርታ እና የንጽሕና ተግባራትን እንዲሁም ይገባኛል የምትልበትን ጸጋ አዘጋጅቼልሃለሁ። ና! ለአንተ መከራ የተቀበልኩትን ያህል በአንተ ደስ ይለኝ ዘንድ ና! የመዳንን ዘውድ እደፋልህ ዘንድ፣ ፍቅሬን እና መንፈስ ቅዱስን በአንተ ላይ አፈስስ ዘንድ፣ እንዲህ አድርጌ ወደ አባቴ አቀርብህ ዘንድ ና! አንተ ከበጎቼ ሁሉ እጅግ ውዱ ነህ፤ እኔ ደሜን እስከመክፈል ደርሼ ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥቼሃለሁና።"
***
የክርስቶስ ስሞች፣ ገጽ 135-36።

ይህን ምሥጢር የሆነ መሐፍ እንድታነቡት ግብዣችን ነው።

ከግዮን.......
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

08 Nov, 06:20


‹‹እንግዲህ የእግዚአብሔር ፍጥረት ሁሉ በጎ እንደሆነ የሚጣልበትም እንደሌለ እንናነገራለን ››አመክንዮ ዘሐዋርያት
‹‹we say further that all the creatures of God are good and there is nothing to be rejected›› apostolic creed
‹‹እግዚአብሔር የምድር አራዊትን እንደ ወገኑ አደረገ፥ እንስሳውንም እንደ ወገኑ፥ የመሬት ተንቀሳቃሾችንም እንደ ወገኑ አደረገ፤ እግዚአብሔርም ያ መልካም እንደ ሆነ አየ። እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። እግዚአብሔርም ባረካቸው፥ እንዲህም አላቸው። ብዙ፥ ተባዙ፥ ምድርንም ሙሉአት። እግዚአብሔርም ያደረገውን ሁሉ አየ፥ እነሆም እጅግ መልካም ነበረ። ማታም ሆነ ጥዋትም ሆነ፥ ስድስተኛ ቀን።›› ዘፍ. 1፡25-31
‹‹ እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም ነውና፥ ከምስጋናም ጋር ቢቀበሉት የሚጣል ምንም የለም።›› 1ጢሞ. 4፡4
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

06 Nov, 04:59


ዛሬ የተነበበው ወንጌል

ማቴዎስ 27
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ሲነጋም የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤
² አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጴንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት።
³ በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደ ተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ፥ ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ፦
⁴ ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ። እነርሱ ግን፦ እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ አሉ።
⁵ ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና ታንቆ ሞተ።
⁶ የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው፦ የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም አሉ።
⁷ ተማክረውም የሸክላ ሠሪውን መሬት ለእንግዶች መቃብር ገዙበት።
⁸ ስለዚህ ያ መሬት እስከ ዛሬ ድረስ የደም መሬት ተባለ።
⁹ በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው፦ ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን፥ የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥
¹⁰ ጌታም እንዳዘዘኝ ስለ ሸክላ ሠሪ መሬት ሰጡት የሚል ተፈጸመ።
¹¹ ኢየሱስም በገዢው ፊት ቆመ፤ ገዢውም፦ የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን? ብሎ ጠየቀው፤ ኢየሱስም፦ አንተ አልህ አለው።
¹² የካህናት አለቆችም ሽማግሎችም ሲከሱት ምንም አልመለሰም።
¹³ በዚያን ጊዜ ጲላጦስ፦ ስንት ያህል እንዲመሰክሩብህ አትሰማምን? አለው።
¹⁴ ገዢውም እጅግ እስኪደነቅ ድረስ አንዲት ቃል ስንኳ አልመለሰለትም።
¹⁵ በዚያም በዓል ሕዝቡ የወደዱትን አንድ እስረኛ ሊፈታላቸው ለገዢው ልማድ ነበረው።
¹⁶ በዚያን ጊዜም በርባን የሚባል በጣም የታወቀ እስረኛ ነበራቸው።
¹⁷ እንግዲህ እነርሱ ተሰብስበው ሳሉ ጲላጦስ፦ በርባንን ወይስ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤
¹⁸ በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
¹⁹ እርሱም በፍርድ ወንበር ተቀምጦ ሳለ ሚስቱ፦ ስለ እርሱ ዛሬ በሕልም እጅግ መከራ ተቀብያለሁና በዚያ ጻድቅ ሰው ምንም አታድርግ ብላ ላከችበት።
²⁰ የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ግን በርባንን እንዲለምኑ ኢየሱስን ግን እንዲያጠፉ ሕዝቡን አባበሉ።
²¹ ገዢውም መልሶ፦ ከሁለቱ ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤ እነርሱም፦ በርባንን አሉ።
²² ጲላጦስ፦ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን እንግዲህ ምን ላድርገው? አላቸው፤ ሁሉም፦ ይሰቀል አሉ።
²³ ገዢውም፦ ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አለ፤ እነርሱ ግን፦ ይሰቀል እያሉ ጩኸት አበዙ።
²⁴ ጲላጦስም ሁከት እንዲጀመር እንጂ አንዳች እንዳይረባ ባየ ጊዜ፥ ውኃ አንሥቶ፦ እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ እናንተ ተጠንቀቁ ሲል በሕዝቡ ፊት እጁን ታጠበ።
²⁵ ሕዝቡም ሁሉ መልሰው፦ ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን አሉ።
²⁶ በዚያን ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ገርፎ ሊሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
²⁷ በዚያን ጊዜ የገዢው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዢው ግቢ ውስጥ ወሰዱት ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ አከማቹ።
²⁸ ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት፥
²⁹ ከእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ፥ በቀኝ እጁም መቃ አኖሩ፥ በፊቱም ተንበርክከው፦ የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት፤
³⁰ ተፉበትም መቃውንም ይዘው ራሱን መቱት።
³¹ ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
³² ሲወጡም ስምዖን የተባለው የቀሬናን ሰው አገኙ፤ እርሱንም መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት።
³³ ትርጓሜው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደሚባለው ስፍራ በደረሱ ጊዜም፥
³⁴ በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፤ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም።
³⁵ ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ፥
³⁶ በዚያም ተቀምጠው ይጠብቁት ነበር።
³⁷ ይህ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው የሚል የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ አኖሩ።
³⁸ በዚያን ጊዜ ሁለት ወንበዶች አንዱ በቀኝ አንዱም በግራ ከእርሱ ጋር ተሰቀሉ።
³⁹ የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና፤-
⁴⁰ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት።
⁴¹ እንዲሁም ደግሞ የካህናት አለቆች ከጻፎችና ከሽማግሎች ጋር እየዘበቱበት እንዲህ አሉ።
⁴² ሌሎችን አዳነ፥ ራሱን ሊያድን አይችልም፤ የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ፥ አሁን ከመስቀል ይውረድ እኛም እናምንበታለን።
⁴³ በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው።
⁴⁴ ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዶች ደግሞ ያንኑ እያሉ ይነቅፉት ነበር።
⁴⁵ ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ።
⁴⁶ በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፦ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም፦ አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው።
⁴⁷ በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው፦ ይህስ ኤልያስን ይጠራል አሉ።
⁴⁸ ወዲያውም ከእነርሱ አንዱ ሮጠ፤ ሰፍነግም ይዞ ሆምጣጤ ሞላበት፥ በመቃም አድርጎ አጠጣው።
⁴⁹ ሌሎቹ ግን፦ ተው፥ ኤልያስ መጥቶ ያድነው እንደ ሆነ እንይ አሉ።
⁵⁰ ኢየሱስም ሁለተኛ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ተወ።
⁵¹ እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤
⁵² መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤
⁵³ ከትንሣኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ገቡና ለብዙዎች ታዩ።
⁵⁴ የመቶ አለቃም ከእርሱም ጋር ኢየሱስን የሚጠብቁ መናወጡንና የሆነውን ነገር አይተው፦ ይህ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ ብለው እጅግ ፈሩ።
⁵⁵ ኢየሱስን እያገለገሉ ከገሊላ የተከተሉት ብዙ ሴቶች በሩቅ ሆነው ሲመለከቱ በዚያ ነበሩ፤
⁵⁶ ከእነርሱም መግደላዊት ማርያምና የያዕቆብና የዮሳ እናት ማርያም የዘብዴዎስም የልጆቹ እናት ነበሩ።

ሰማይና ምድር ያልፋሉ ቃሌ ግን አያልፍም እንዳለ ኢየሱስ ክርስቶስ

እውነት ለሁሉ

05 Nov, 15:48


የወይን ጠጅ መጥፎ የመጠጥ ፍጥረት ነው ያለማስተዋል የሚጻፍ መጣጥፍ እስከ መዘዙ

ለሚመለከተው አድርሱለት ተብላችኃል

https://vm.tiktok.com/ZMh4q3VL6/

እውነት ለሁሉ

05 Nov, 08:14


ውይይት


ሥላሴ በመፅሐፍ ቅዱስ እና በአበው
በአይሁድ ትውፊት 🖋

👤ወንድም ቅዱስ
👤ወንድም ዴቭ
👤ወንድም አላዛር
👤ወንድም ብሩክ

ይደመጥ

እውነት ለሁሉ

04 Nov, 17:27


እግዚአብሔር ጠባቂያችን ነው !!


እግርህን ለመናወጥ አይሰጠውም፤ የሚጠብቅኽም አይተኛም። እነሆ፥ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም አያንቀላፋምም። እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፥ እግዚአብሔርም በቀኝ እጅኽ በኩል ይጋርድሃል። ፀሐይ በቀን አያቃጥልህም ጨረቃም በሌሊት። እግዚአብሔር ከክፉ ኹሉ ይጠብቅሃል፥ ነፍስኽንም ይጠብቃታል። ከዛሬ ጀምሮ እስከ ዘላለም እግዚአብሔር መውጣትህና መግባትኽን ይጠብቃል። መዝ121 : 3-8

ዋስትናና ሰላም በሌላት ዓለም መካከል ሊጠብቀን ኪዳን የገባልን እግዚአብሔር ነው።የእግዚአብሔር ጥበቃ ከእኛ ጋር ነው።

በዙርያችን እየሆነ ካለው ነውጥና ረብሻ የተነሳ ምናልባት ፍርሃት ውስጥ ልንዋጥ እንችል ይሆናል። በዚህ ኹሉ ግን የጌታን ስም እንጥራ እንዲህ እንበለው የሚጠብቀኝ አይተኛም አያንቀላፋም።

እግዚአብሔር እንደሚጠብቀን የነገረን የሚጎዳ ነገር ባለበት ዓለም ውስጥ ነው። በነውጥ ጊዜ፣በሞትና ፣በጭንቀት በበሽታና በሥቃይ በማግኘትና በማጣት ነው። በእኛ መካከል አንድ እርምጃ ቢቀር እንኳን ጌታ ሳያቋርጥ ይጠብቀናል።

ይኽን አስደናቂ ጥበቃ ተማምነን በልበ ሙሉነት ሥራችንን እንሥራ፣ ትምህርታችንን እንማር፣ አገልግሎታችንን እናገልግል ማንም ምንም አይጎዳንም።ምንም አንኾንም።ስንወጣ ስንገባ የእግዚአብሔርን ጥበቃ እንረዳ፣ እናውጅ፣ እንተማመን በርሱም እንደገፍ ፣ሰላም ይሰማን።

ምክንያቱም እግዚአብሔር አልከበደውም!!!!


👉 የሳራ እና የአብርሃም ማርጀት እግዚአብሔር በእነርሱ ያሰበውን እና ያቀደውን ከማድረግ አልከበደውም ።

👉የዮሴፍ ያየውን ህልም ወንድሞቹ ቢሸጡት እግዚአብሔር መንገድ አድርጎት ህልሙን እውን ማድረግ አልከበደውም ።

👉 የፈርኦን ልብ መደንደን እስራኤላውያንን ከ ግብፅ ምድር ማውጣት እና የቀይ ባህር መሙላት ከፍሎ ማሻገርን እግዚአብሔር አልከበደውም ።

👉 የዳዊት እረኛ እና ልጅ መሆኑ አስፈሪውን ለእስራኤል ጭንቅ የሆነውን ጎልያድን መግደል ከዛን ለንግስና ማብቃት  እግዚአብሔር አልከበደውም ።


👉 የዳንኤል በአንበሶች ጉድጓድ መጣል  እግዚአብሔር የአንበሶችን አፍ መዝጋት አልከበደውም ።

👉 በሲድራቅ፣ በሚሳቅና አብደናጎን(አናንያ ፣አዛርያና ሚሳኤል( ከእሳት ውስጥ ሆነው ከመቃጠል ማዳን አልከበደውም ።


👉 ክርስቶስ በደቀ መዛሙርቱ ላይ ምንም አይነት መከራ ስደት እስራት መገደል ቢበዛባቸው ክርስቶስ በእነርሱ ላይ መታየት አልከበደውም ።

👉 አሳዳጅ የነበረውን ሳኦልን ለውጦ ለክርስቶስ እንዲኖር ማድረግ እና ክርስቶስን እንዲያውቅ ማድረግም አልከበደውም ።

👉 በእስር ቤት በቤተክርስቲያን በደሴት ብቻ በሁሉም አህጉራት እርሱን ባመኑት ላይ መገለጥ እና መታየት አልከደውም ።


👉 የነበረም ያለ የሚመጣ ችግር በእናንተ ላይ ያቀደውን እቅድ መፈፀም አይከብደውም አልከበደውም።

“የሰላምም አምላክ ራሱ ሁለንተናችሁን ይቀድስ፤ መንፈሳችሁም ነፍሳችሁም ሥጋችሁም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጣ ጊዜ ያለ ነቀፋ ፈጽመው ይጠበቁ።" 1ኛ ተሰ 5፥23 አሜን🥰

………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!


ይቆየን

እውነት ለሁሉ

04 Nov, 07:26


Augustine
“Christ was carried in his own hands when, referring to his own body, he said, ‘This is my body’ [Matt. 26:26]. For he carried that body in his hands” (Explanations of the Psalms 33:1:10 [A.D. 405]).
“I promised you [new Christians], who have now been baptized, a sermon in which I would explain the sacrament of the Lord’s Table. . . . That bread which you see on the altar, having been sanctified by the word of God, is the body of Christ. That chalice, or rather, what is in that chalice, having been sanctified by the word of God, is the blood of Christ” (Sermons 227 [A.D. 411]).

“What you see is the bread and the chalice; that is what your own eyes report to you. But what your faith obliges you to accept is that the bread is the body of Christ and the chalice is the blood of Christ. This has been said very briefly, which may perhaps be sufficient for faith; yet faith does not desire instruction” (ibid., 272).

እውነት ለሁሉ

03 Nov, 08:45


ሰኞ ከምሽቱ 2:00 ሠዓት

ልጅ ብሩክ ቤት👉 https://vm.tiktok.com/ZMhXrGNmW/

እውነት ለሁሉ

02 Nov, 14:15


ስለ መሲሑ አምላካችን በብሉይ ኪዳን ትንቢት በሀዲስ ኪዳን ደሞ ፍጻሜ ላሳያችሁ ❤️❤️🙏

እውነት ለሁሉ

02 Nov, 10:21


https://t.me/Astemeheroteewnet
.

እውነት ለሁሉ

02 Nov, 07:29


"የክርስቶስ ቤዛነት ይህ ነው፦ እርሱ ስለተሸከማቸው ዘግናኝ ሕማሞች እና ኃጢኣቶች እስካሁን ድረስ ያለማቋረጥ ይናገራል። ኃጢኣት የማያውቀውን እርሱን እግዚአብሔር አብ ስለእኛ ሲል 'ኃጢኣት እንዲሆን' አደረገው። አመንዝራው፣ ስድ ሆኖ የሚበድለው፣ ቆሻሻ በሆኑ ተግባራት አረንቋ ውስጥ የሚዛቅጠው እና ኃፍረት አልባ በሆኑ ተግባራት የሚበላሸው ሁሉ ከክርስቶስ ሲሸሽ ድምጹ በኋላው ይከተለዋል። ይኸውም 'የተወደድህ ልጅ ሆይ፥ ና! ኃጢኣቶችህ ከእኔ ጋር ናቸው፤' እያለ የሚጣራ የእግዚአብሔር ልጅ ደም ነው! ገና የሠራሃቸው ዕለት ነው በምልዓት የተሸከምኳቸው። ካሣውን ከፍያለሁ፦ ሐፍረት ተጭኖብኛል፤ ተገርፌያለሁ፤ ደቅቄያለሁ፤ ተሰቅያለሁ፤ እንዲሁም መርገምን ተሸክሜያለሁ። ለአንተ የይቅርታ እና የንጽሕና ተግባራትን እንዲሁም ይገባኛል የምትልበትን ጸጋ አዘጋጅቼልሃለሁ። ና! ለአንተ መከራ የተቀበልኩትን ያህል በአንተ ደስ ይለኝ ዘንድ ና! የመዳንን ዘውድ እደፋልህ ዘንድ፣ ፍቅሬን እና መንፈስ ቅዱስን በአንተ ላይ አፈስስ ዘንድ፣ እንዲህ አድርጌ ወደ አባቴ አቀርብህ ዘንድ ና! አንተ ከበጎቼ ሁሉ እጅግ ውዱ ነህ፤ እኔ ደሜን እስከመክፈል ደርሼ ከፍ ያለ ዋጋ ሰጥቼሃለሁና።"
***
የክርስቶስ ስሞች፣ ገጽ 135-36።

………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
በግዮን የተጻፈ

እውነት ለሁሉ

02 Nov, 05:30


“ይህ ምሥጢር ታላቅ ነው፥ እኔ ግን ይህን ስለ ክርስቶስና ስለ ቤተ ክርስቲያን እላለሁ።” ኤፌ 5፥32
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

እውነት ለሁሉ

31 Oct, 16:10


መታየት፣በገዛ ደም መግባት፣ .......ምን ማለት ነው?
በዲያቆን ሸዋፈራው
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!!

እውነት ለሁሉ

31 Oct, 16:10


ሊቀካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ!
ሊቀ ካህናት ሲባል ምን ማለት ነው?
በዲያቆን ሸዋፈራው
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

31 Oct, 15:54


ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ስለ ድንግል ማርያም...!
"አንቺ የተከበርሽ የተደነቅሽ ድንግል ሆይ ከየትኛውም ታላቅነት በላይ ታላቅ ነሽ፤ እንዳንቺ ያለ ታላቅነት ያለው ርሱ ማን ነው? አንቺ የእግዚአብሔር ወልድ ማደሪያ ድንግል ሆይ ከፍጥረታት መኻከል ከማን ጋር ላወዳድርሽ? ከኹሉም በላይ ታላቅ ነሽ፤ የዐዲስ ኪዳን ታቦት ወርቅን ሳይኾን ንጽሕናን የተጐናጸፍሽ! እውነተኛው መና በውስጧ ያኖረችው መሶበ ወርቅ የተቀመጠባት ታቦት ነሽ ይኸውም ሥጋን የተዋሐደው መለኮት ነው፤ ከለመለመችው ምድርና ከፍሬዋ ጋር ላነጻጽርሽን? ግን አንቺ ኹሉንም ትልቂያቸዋለች ምክንያቱም “ምድር የእግሬ መረገጫ ናት” ተብሎ ተጽፏልና (ኢሳ 66፡1)
O noble Virgin, truly you are greater than any other greatness. For who is your equal in greatness, O dwelling place of God the Word? To whom among all creatures shall I compare you, O Virgin? You are greater than them all. O Covenant, clothed with purity instead of gold! You are the Ark in which is found the golden vessel containing the true manna, that is, the flesh in which divinity resides. Should I compare you to the fertile earth and its fruits? You surpass them, for it is written: “The earth is my footstool” (Is 66:1).
ነገር ግን አንቺ ፍጹም የኾነውን የባሕርይ አምላክ እግር፣ ራስ እና መላ አካል ይዘሻልና፤ ሰማይ ታላቅ የኾነ ቢኾንም ግን ያንቺ አቻ አይኾንም “ሰማይ ዙፋኔ ነው” ተብሎ ተጽፏልና (ኢሳ 66፡1)፤ አንቺ ደግሞ የአምላክ ማደሪያ ነሽ፤ መላእክት እና የመላእክት አለቆች ታላቅ ናቸው ብልም አንቺ ከኹሉም ታላቅነት በላይ ነሽ፤ ይኸውም መላእክት እና ሊቃነ መላእክት ባንቺ ማሕፀን ላደረው ለርሱ በረአድ የሚያገለግሉ በመኾናቸው በፊቱ መናገር የማይችሉትን አንቺ በነጻነት ታናግሪዋለሽ፡፡ ኪሩቤልን ታላቅ ናቸው ብንልም አንቺ ከነርሱ ታላቅነት በላይ ነሽ፤ ኪሩቤል የእግዚአብሔርን ዙፋን ይሸከማሉ (መዝ 80፡1፤ 99፡1)፤ አንቺ ግን እግዚአብሔርን በእጅሽ ያዝሽው፤ ሱራፌልንም ታላቅ ናቸው ብልም አንቺ ከነርሱ ታላቅነት በላይ ታላቅ ነሽ፤ ሱራፌል በክንፎቻቸው ፊታቸውን ይሸፍናሉ (ኢሳ 6፡2)፤ ፍጹም የኾነውን ጌትነቱን ማየት አይችሉም አንቺ ግን ፊቱን እያየሽ እና እየዳሰስሽ ጡትን በከበረ አፉ ውስጥ አጥብተሻልና ከነርሱ ትልቂያለሽ፡፡
But you carry within you the feet, the head, and the entire body of the perfect God. If I say that heaven is exalted, yet it does not equal you, for it is written: “Heaven is my throne” (ibid.), while you are God’s place of repose. If I say that the angels and archangels are great—but you are greater than them all, for the angels and archangels serve with trembling the One who dwells in your womb, and they dare not speak in his presence, while you speak to him freely. If we say that the cherubim are great, you are greater than they, for the cherubim carry the throne of God (cf. Ps 80:1; 99:1), while you hold God in your hands. If we say that the seraphim are great, you are greater than them all, for the seraphim cover their faces with their wings (cf. Is 6:2), unable to look upon the perfect glory, while you not only gaze upon his face but caress it and offer your breasts to his holy mouth….
ሔዋን የሙታን እናት ናት “ኹሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲኹ ኹሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይኾናሉና” (1ቆሮ 15፡22) እንደተባለ፤ ሔዋን ከዛፍ ፍሬ ወስዳ ባሏ ከርሷ ጋር እንዲበላ አድርጋለች፤ በዚኽ ምክንያት እግዚአብሔር “ከዚኽ በበላችኊ ጊዜ ትሞታላችኊ” ካላቸው ዛፍ በሉ (ዘፍ 2፡17)፤ ሔዋን ፍሬውን ወስዳ የተወሰነውን በልታ የተወሰነውን ለባሏ ሰጠችው፤ ርሱም በላው ሞተም፡፡ አንቺ ብልኅ ድንግል ሆይ በአንቺ ግን የእግዚአብሔር ልጅ የኾነው የሕይወት ዛፍ ዐደረ፤ በእውነትም አካሉን ሰጥቶናል እኛም ከርሱ በልተናል፤ ሕይወት ለኹሉም እንዲኽ ተሰጠ፤ ባንቺ በተወደደው ልጅሽ በእግዚአብሔርነቱ ምሕረት ኹሉም ወደ ምሕረት መጣ፤ በዚኽም ምክንያት ነው መንፈስሽ በአምላክሽ በመድኀኒትሽ ሐሤት ያደረገው"
As for Eve, she is the mother of the dead, “for as in Adam all die, even so in Christ shall all be made alive” (1 Cor 15:22). Eve took from the tree and made her husband eat of it along with her. And so they ate of that tree of which God had told them: “The day you eat of it, you shall die” (Gen 2:17). Eve took from it, ate some of it, and gave some to her husband with her. He ate of it, and he died. In you, instead, O wise Virgin, dwells the Son of God: he, that is, who is the tree of life. Truly he has given us his body, and we have eaten of it. That is how life came to all, and all have come to life by the mercy of God, your beloved Son. That is why your spirit is full of joy in God your Savior!
St. Athanasius, Fourth Century Homily of the Papyrus of Turin, ed. T. Lefort, in Le Muséon 71 (1958): 216-217 .
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

31 Oct, 09:23


የመጀመሪያችን ክርስቶስ ኢየሱስ🥰
~~
ምንፍቅና ቅጥ የለውም ከመሰረታው የአስተምሮ ፍልሰት
ጀምሮ እስከ አገላልጽ ድረስ ለጆሮ የሚሰቀጥጥ ሆኗል።
ከሐዋርያት ጀምሮ ከቶውንም ያልተጠቀሙባቸውን እንግዳ
ቃላት መስማት የክህደት ትልቁ መገለጫ ሆኗል።
ሉተራዊነት መጽሐፍ ቅዱስን ማንም ሰው እንደገዛ
አስተሳሰቡ ይተርጉም የሚል መርህ የያዘ ክርስትናን
የሚቃረን ርዕዮተ አለም ነው።በዚህ የአስተሳሰብ ድቀትም
ብዙዎች ከእውነት መንገድ ስተው የአጋንንትን ትምህርት
አያደመጡ ነው።
ይህን እንደ መንደርደርያ ልል ያነሳሳኝ ጌታችን እኛን
ለማዳን በአትህቶ ርዕስ በስጋዌ ይፈጸማቸውን ተግባራት
በቅጡ ባለመረዳት ክብር ምስጋና ይግባውና ከክብሩ ዝቅ
አርገው እንደፍጡር ወንድሜ እንዲሁም ደረጃውን
ባልጠበቁ ቃላት እስከ ማቆላመጥ መደረሱ በስመ እምነት
የሚፈጸም ከፍተኛ ዝቅጠት መሆኑን ማስረዳቱ ተገቢ
መስሎ ስለታየኝ ነው።
፨፨ በኲራችን ክርስቶስ፨፨፨
በመሰረቱ ክርስቶስ በኲር ተብሎ የተጠራው ለእኛ ወንድም
ስለሆነ አይደለም ምንም እንኳን ፍጹም ሰው መሆኑን
ለማረጋገጥ እርሱ ወንድሞቼ ብሎ ቢጠራንም እኛ ግን
ወንድማችን ብለን እንጠራው ዘንድ መጽሐፍ ቅዱስ
አያዘንም።
ወንድሜ ብሎየጠራውም ሐዋርያ የለም ይህ ድፍረትም
ትዕቢትም ነውና።እርሱ ፍጹም ሰው መሆኑን ለማረጋገጥ
የተናገራቸው ብዙ የትህትና ቃላት አሉ ለምሳሌ ጌታ
በመስቀል ላይ
"አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ "ማር15:35 ብሏል
እንግዲህ እርሱ አምላኬ አምላኬ ብሏል ተብሎ ክርስቶስ
አምላክ አለው ብሎ መናገር ክህደት ነው
የሚሆነው።በሌላም ስፍራ ትህትናን እና ከውዳሴ ከንቱ
መራቅን ለማስተማር
"ኢየሱስም ስለምን ቸር ትለኛለህ ከአንዱ ከእግዚአብሔር
በቀር ቸር የለም "ማር10:18። ይላል እንግዲህ ይህንን
ይዞ ክርስቶስ ቸር አይደለም እግዚአብሔርም አይደለም
ለማለት የሚደፍር ሴይጣን ካልሆነ ማነው?
ልክ እንደዚሁ ወንድሞቼ ብሎ ጠርቶናል ብሎ ለስም
አጠራሩ ክብር ውዳሴ ስግደትና አምልኮት የሚገባውን
ክርስቶስን ወንድሜ ብሎ መጥራት አምላክ ሰው
የሆነበትን አላማ አለመረዳትና የአጋንንት አስተምሮ ሰለባ
የመሆን ውጤት ነው።
ታድያ ክርስቶስ በኲር ሲባል ምን ማለት ነው? በኲር
የሚለው ለክርስቶስ ሲነገር ለሌሎች ፍጡራን
እንደሚገለጸው አይደለም። ክርስቶስ አባቱን አብን በመልክ
የሚመስለው በባህሪ የሚተካከለው ልጁ ነው
በመልክ መምሰሉን ሲገልጽ
"እኔን ያየ አብን አየ" ዮሐ14:9
ይላል። በክብር መተካከሉንም ሲገልጽ
"አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነውን
ክብሩን አየን" ዮሐ1:14 ይላል እንግዲህ ለአብ በመልክ
የሚመስለው በባህርህ የሚተካከለው ልጁ አንድ እና አንድ
ወልድ ብቻ ነው መጽሐፍ ቅዱስም ይህን ሲያረጋግጥ
እንዲህ ይላል
"በአባቱ እቅፍ ያለ አንድ ልጁ ተረከው" ዮሐ1:18
በሌላም ቦታ
"አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ዓለሙን ውዶአልና" ዮሐ3:16
ስለዚህ ክርስቶስ በኲር የተባለው ታናሽ ወንድም ስላለው
አይደለም እርሱ ለአባቱ ለአብ አንድያ ለእናቱም ለድንግል
ማርያምም አንድያ ልጅ ነው ።
ክርስቶስ ብኲርና ግን የተልየ ትርጉም አለው
፨ እርሱ ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኲር ነው
"ከፍጥረት ሁሉ በፊት በኲር ነው" ቆላ 1:15-16
ይህ ቃል እንደሚያስረዳን በኲር የሚለው ለክርስቶስ
አለም ሳይፈጠር ዘመን ሳይቆጠር የነበረ ቀዳማዊ ማለት
ነው በሌላ አገላለጽ የፊተኛው የሚል ትርጉም አለው
ማለት ነው እርሱ ክርስቶስ ፊተኛውም ኋለኛውም
ተብሏልና ራእ 22:13
፨የትንሳኤችን በኲር ነው
"እርሱም በሁሉ ፊተኛ ይሆን ዘንድ መጀመርያ ከሙታንም
በኩር ነው" ቆላ 1:18
"ከሙታንም በኲር የምድርም ነገስታት ገዥ"ራእ1:4-5
ስለዚህ ክርስቶስ የትንሳኤያችን በኲር የክርስትናችን ፊተኛ
ቀዳሚ መስራችና ተምሳሌታችን ስለሆነ በኲር ይባላል ።
ዲያቆን ሸዋፈራው
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

31 Oct, 08:57


ብጽዕት ድንግል ማርያም!

ለእግዚአብሔር አብ ፈቃድ ለልጁ ለኢየሱስ የማዳን ሥራ ለእያንዳንዱም የመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት ሙሉ በሙሉ በመታመኗ ድንግል ማርያም የቤተክርስቲያን የእምነት እና የፍቅር አብነት ነች ሉቃ1:45፡፡ስለሆነም እርሷ የቤተክርስቲያን አካል ነች፡፡በእርግጥም እርሷ ቀደምትና ሙሉ በሙሉ ልዮ የሆነች የቤተክርስቲያን አማናዊ ተምሳሌት ናት፡፡

ከቤተክርስቲያን እና ከመላው የሰው ዘር ጋር ካላት ግንኙነት አንጻር ሚናዋ ከዚህም የላቀ ነው፡፡ፍጹም ልዮ በሆነ መንገድ መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ነፍሳትን እንደገና መለኮታዊ ሕይወት ለማጎናጸፍ በሚያከናውነው ተግባር እርሷ በታማኝነቷ በተስፋዋ እና በጽኑ ፍቅር ተባብራለች ስለዚህ በተቀዳጃቸው የጸጋ ማዕረግ እናታችን ናት፡፡ይሀህ ጸጋ የተሞላው የማርያም ድንግል እናትነት ብሥራቱን ሰምታ ታማኝነት ቃል ከገባችበትና በመስቀል ሥር ሳትጠራጠር ቆማ ከቆየችበት ጊዜ አንስቶ የተመረጡት ሁሉ ዘላለማዊ ሕይወት እስከሚያገኙበት ጊዜ ድረስ ሳያቋርጥ ይቀጥላል፡፡ሉቃ1:26-45, ዮሐ19:26፡፡ወደ ሰማይ በተወሰደችበት ጊዜም ይህን የአማላጅነት ሥራዋን አልተወችም ዮሐ2፡፡በአያሌዎቹ የአማላጅነት ሥራዎቿ የዘላለም ደኅንነት በረከቶችን ለእኛ ማስገኘቷን ቀጥላለች ፡፡ስለሆነም ቤተክርስቲያን ቡርክት ድንግል : በአማላጅነቷ ደጋፊ :እመ ብርሃን: ወዲተ አምላክ: በጸሎቷ የምትረዳ ...... በሚሉ
ማዕረጎች ትማጸናታለች፡፡

የድንግል ማርያም እናት እና አማላጅ መሆን ብቸኛ የሆነው የጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አስታራቂነት በምንም አይነት መንገድ አያደበዝዘውም ይልቁንም አማላጅነቷ ኃይሉን ሁሉ ከዚሁ ያገኛል፡፡አንድም ፍጡር መቼም ቢሆን ሥጋን ከተዋሃደው ቃል እና መድኃኒት ከሆነው ጌታ ኢየሱስ ጋር እኩል ሊሆን አይቻለውም፡፡ልክ የክርስቶስ ክህነት : ብርሃንነት:አምላክነት: አስታራቂነት.... ባለሟሎቹ እና ምእመናን በልዮ ልዮ አይነት ጸጋ መንገዶች እንደሚጋሩና የእግዚአብሔር ፍቅር በተለያዮ መንገዶች በፍጥረቱ መሃል እንደሚያበራ ሁሉ በአዳኙ በክርስቶስ ልዮ አስታራቂነት ከዚህ አንድ ምንጭ የመጋራትን ዘርፍ ብዙ ትብብር አካልን ይፈጥራል እንጂ አያግድም፡፡የእግዚአብሔር መልአክ ባበሰራት ጊዜ እንደ ቃልህ ይሁንለልኝ በማለት ሉቃ 1:38 እሽታዋን በመግለጽ ልጇ በሚያከናውነው ሥራ ሁለሉ ከጅምሩ ማርያም ተባባሪ ሆናለች ፡፡የዓለም ቤዛና የምሥጢራዊው አካል ራስ በሆነበት ሥፍራ ሁሉ እርሷ እናት ናች፡፡እጅግ ብጽዕት ሉቃ1:49 ድንግል ማርያም በምድር ላይ ያሳለፈችው ሕይወቷ እንዳበቃ የአካሉ ክፍሎች ሁለሉ ከሞት እንደሚነሱ በማመላከት በልጇ ትንሳኤ ክብር ወደ ተጎናጸፈችበት መንግስተ ሰማይ በነፍስና በሥጋ ተወሰደች ፡፡ቅድስት ወላዲተ አምላክ አዲሲቷ ሔዋን የቤተክርስቲያን እናት በሰማይ ቤትም ስለ ክርስቶስ አካል ክፍሎች እናትነቷን እነንደምትቀጥል የታመነ ነው፡፡ ምለልጃዋ በረከቷ እናትነቷ በሁላችን ይጽናብን የልጇ ቸርነት አይለየን !! አሜን፡፡
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
ዲያቆን ሸዋፈራው
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

31 Oct, 05:51


እንዴት ነው ምንግባባው ወገን 🤔

እውነት ለሁሉ

30 Oct, 18:20


“የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና(መከራ ትቀበሉ ዘንድ) ፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።”1ኛ ጴጥ 2፥21
"ወዳጄ ሆይ መስዬ የምናገረውን ነገር በዓይነ ልቡና አስተውል! አንድ የሚነግሥ የንጉሥ ልጅ በእናቱ ማኅፀን ሳለ ምንም እንደማያውቅና ከተወለደ በኋላ ግን እንደሚነግሥ እንደሚገዛ ሁሉ የአሁኑ ጊዜና የመንግሥተ ሰማይ ሥርዓትም እንዲህ ነው፡፡ እነሆ ታሥሮ በመከራ በኃዘን የሚኖር ሰው፣ ልዩ ልዩ የሚሆን ፅኑ መከራ የተፈራረቀበት ሰው በኋላ ከመከራ አውጥተው ከእስራት ፈትተው አንግሠዉት የነገሠ ሰው ደስ እንደሚለው የመንግሥተ ሰማይ ተድላ ደስታም እንዲህ ነው፡፡

ሆኖም ግን እስከ አሁን ድረስ የተካከለ ምሳሌ መስዬ ማስረዳት አልተቻለኝም፡፡ አንድ ሁሉንም ነገር (ንግሥናም ቢሆን) በዚህ ዓለም ያገኘ ሰው በመጀመርያይቱ ዕለት፣ አዋጅ በነገሩለት ቀን፣ ሹመት ያዳብር ባሉት ዕለት፣ እጅ መንሻ ባገቡለት ጊዜ መጠን በመጠን ደስታው እየበዛለት ይሄዳል፡፡ ሆኖም ግን ይህም የመንግሥተ ሰማይን ነገር በሚገባ የሚያስረዳ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ይህ ሰው ያገኘው ሁሉ ኃላፊ ጠፊ ስለሆነ እየለመደው እየሰለቸው ይሄዳልና፡፡ መንግሥተ ሰማያት ግን ፍቅሯ በልቦና ፀንቶ ይኖራል እንጂ በመሰጠቷ አትፈጸምም፤ አትለወጥም፤ አትሰለችም ኅልፈት፣ መለወጥ፣ ፍጻሜ በሌለባት በመንግሥተ ሰማያት ያለ ጣዕም፣ ተድላ፣ መዓዛ ብርሃንን ያገኘች የነፍስማ አኗኗርዋ እንደምን ይሆን? የማታልፍ፣ ሐዘን ሁሉ ፀዋትወ መከራ የሌለባት፣ ከነውር ከነቀፋ ከመቆርቆር ንጽሕት የምትሆን፣ ደስታን ፍጹም ተድላን የተመላች፣ በትሩፋት ሥራ የሚገኘውን ክብር ልዕልናን የተመላች መንግሥተ ሰማያት እየፀናች ትሄዳለች እንጂ ፍጻሜ መለወጥ የለባትም"ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
https://t.me/orthodoxawitewahdo

እውነት ለሁሉ

30 Oct, 12:20


የጴንጤ ለውጥ ወደ እውነታ ✈️ አሪፍ ነው ብለናል እኛምኮ እውነታን አንካድ ነው ምንለው🙏

እውነት ለሁሉ

29 Oct, 19:47


❤️❤️
#የስደት_ስንቅ ፨፨፨

"ሕፃኑን እና እናቱን ይዘህ ሽሽ"
ማቴ 2:13
ብዙውን ጊዜ ስደት ሽሽት ጉዞ ስንቅ ሲታሰብ ስንቅ የማይረሳ ነገር
ነው።ምግም
እና መጠጥ በስንቅነት የተለመዱ ናቸው ። ሕፃኑን እና እናቱን ይዞ
መስደድ ግን
መታደል ነው።እውነትም ምግብ በአገልግል ለስደት ይመቻል በአገልግል
በመሶብ ያለ ምግብ ጣዕሙ ልዩ በተለይም በስደት ሲመገቡት ድካምን
ያርቃል ኃይልም ጉልበትም ይሆናል ።እስራኤልም መና ያለባትን መሶበ
ወርቅ
ይዘው በመቅደስ አስቀምጠው ይጓዙ እንደነበር መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ
እያለ
ይገልጻል
"በእርሷም ውስጥ መና ያለባት የወርቅ መሶብና የበቀለች የአሮን በትር
የኪዳኑም ጽላት ነበሩ" ዕብ9:4
የሕይወት ስንቅ መና
"""""""""""""""""""""""""""
የክርትናችን የሕይወት ስንቅ መና ክርስቶስ ነው
"ከሰማይ የወረደ የሕይወት መና እኔ ነኝ" ዮሐ6:51
አዎን የሕይወታችን ስንቅ ከጸጋ መራባችንን ያራቀልን ከሞትም ያተረፈን
የሕይወት መና ክርስቶስ ነው ከእርሱ የሚበላ በእርሱ ይኖራል
"ስጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጧ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ
እኖራለሁ"ዮሐ6:56-57
በክርስቶስ ለሚኖር የመሻቱ ሁሉ ስኬት አያጠራጥርም
"በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ለምኑ
ይሆንላችሁማል"
ዮሐ15:7
፨የስንቅ መሶበ ወርቅ ዘመና፨
''""""""""""""""""""""""""""""""""""
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ በውዳሴ ማርያምድንግልን ሲያወድሳት
"አንቲ ውእቱ መሶ በወርቅ ንጹሕ እንተ ውስቴታ መና ኅቡእ ኅብስት
ዘወረደ
እምሰማያት ወሀቤ ሕይወት ለኲሉ ዓለም" ዘሰንበት
ለዓለም ሁሉ ሕይወትን የሚያድለው መናን ክርስቶስ ይለብሽ የወርቅ
መሶብ
አንቺ ነሽ አላት ።አዎን ስንቅ ያለ መሶብ አይሆንም በቤተ መቅደስም
ሲቀመጥ
መናው ብቻ አልነበረም ከነ መሶበ ወርቁ ነው ። ወርቅ የንጽሕናዋ ምሳሌ
ነው
ንጹሀ ባህሪ ለሆነው መና ንጹሕ መሶበ ወርቅ ግድ ይላል ። በቤተ
መቅደሱ
መናው ከነ መሶበ ወርቁ መቀመጡ ዛሬም የክርስቶስ በሆነው ቤተመቅደስ
አማናዊው መና ክርስቶስ እና መሶበ ወርቅ እናቱ መኖራቸው መታየታቸው
መነገራቸው መሰበካቸው ግድ ነው።የእያንዳንዳችን ሰውነትም የእርሱ
ቤተመቅደስ ነው በልባችን ሁል ጊዜ መናውን ከነመሶበ ወርቁ ስንቅ ይዘን
መጓዝ የእስራኤል ዘነፍስም የክርስትያኖች የስደት ስንቅ ነው ሕፃኑ መና
ሲሆን
እናቱ መሶበ ወርቅ ናት ሕፃኑና እናቱን ይዘህ ሽሽ እንደተባለ እኛም
በስደታችን
ስንቅ ልናደርጋቸው ይገባል። እናቱን እና ልጇን ስንቅ ያረገ በቤቱ ያኖረ
የጓዳው
ባዶነት አይስጨንቀውም በጎደለ የምታሳስብ በጎደለም የሚሞላ ለበረከትና
በረከት የሚሆኑ ናቸውና።
፨፨፨፨የስደት ስንቅ፨፨፨፨፨
ዲያቆን ሸዋፈራው አለነ
@orthodoxytewahedo

እውነት ለሁሉ

29 Oct, 08:45


“ቅዱሳን........ራሳቸውም ስለ እናንተ ሲያማልዱ፥ በእናንተ ላይ ከሚሆነው ከሚበልጠው ከእግዚአብሔር ጸጋ የተነሣ ይናፍቁአችኋል።”2ኛ ቆሮ 9፥14
“saints....And by their prayer for you, which long after you for the exceeding grace of God in you.”2 Corinthians 9፥14 (KJV)
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

እውነት ለሁሉ

27 Oct, 18:22


ስንቶቻችን የሰማንያ አሀዱ(81)
መጽሐፍ ቅዱስ አቆጣጠር እናውቃለን?
የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት 46 ናቸው አቆጣጠራቸውም እንደሚከተለው ነው
1 ኦሪት ዘፍጥረት
2 ኦሪት ዘጸአት
3 ኦሪት ዘኁልቁ
4 ኦሪት ዘሌዋውያን
5 ኦሪት ዘዳግም
6 መጽሐፈ ኩፋሌ
7 መጽሐፈ ኢያሱ
8 መጽሐፈ መሳፍንት
9 መጽሐፈ ሩት
10 መጻሕፍተ ሳሙኤል
11 መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ
12 መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ
13 ዜና መዋዕል ቀዳማዊ
14 ዜና መዋዕል ካልዕ
15 መጽሐፈ ሄኖክ
16 መጽሐፈ ዕዝራ
መጽሐፈ ነህምያ
17 መጽሐፈ ዕዝራ ሱቱኤል
መጽሐፈ ዕዝራ ካልዕ
18 መጽሐፈ ጦቢት
19 መጽሐፈ ዮዲት
20 መጽሐፈ አስቴር
21 መጻሕፈተ መቃብያን /ቀዳማዊ ካልዕ/
22 መቃብያን ሣልስ
23 መጽሐፈ ኢዮብ
24 መዝሙረ ዳዊት
25 መጽሐፈ ምሳሌ
26 መጽሐፈ ተግሣጽ
27 መጽሐፈ መክብብ
28 መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን
29 መጽሐፈ ጥበብ
30 መጽሐፈ ሲራክ
31 ትንቢተ ኢሳይያስ /ጸሎተ ምናሴን ጨምሮ/
32 ትንቢተ ኤርምያስ
ሰቆቃወ ኤርምያስ
ተረፈ ኤርምያስ
መጽሐፈ ባሮክ
ተረፈ ባሮክ
33 ትንቢተ ሕዝቅኤል
34 ትንቢተ ዳንኤል
መጽሐፈ ሶስና
ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅ
ተረፈ ዳንኤል
35 ትንቢተ ሆሴዕ
36 ትንቢተ አሞጽ
37 ትንቢተ ሚክያስ
38 ትንቢተ ኢዮኤል
39 ትንቢተ አብድዩ
40 ትንቢተ ዮናስ
41 ትንቢተ ናሆም
42 ትንቢተ ዕንባቆም
43 ትንቢተ ሶፎንያስ
44 ትንቢተ ሐጌ
45 ትንቢተ ዘካርያስ
46 ትንቢተ ሚልክያስ
የአዲስ ኪዳን መጽሕፍት 35 ናቸው አቆጣጠራቸውም እንደሚከተለው ነው
1 የማቴዎስ ወንጌል
2 የማርቆስ ወንጌል
3 የሉቃስ ወንጌል
4 የዮሐንስ ወንጌል
5 የሐዋርያት ሥራ
6 ወደ ሮሜ ሰዎች
7 የመጀመሪያይቱ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች
8 ሁለተኛይቱ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች
9 ወደ ገላትያ ሰዎች
10 ወደ ኤፌሶን ሰዎች
11 ፊልጵስዩስ ሰዎች
12 ወደ ቆላስይስ ሰዎች
13 የመጀመሪያይቱ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች
14 ሁለተኛይቱ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች
15 የመጀመሪያይቱ ወደ ጢሞቴዎስ
16 ሁለተኛይቱ ወደ ጢሞቴዎስ
17 ወደ ቲቶ
18 ወደ ፊልሞና
19 ወደ ዕብራዊያን ሰዎች
20 የመጀመሪያይቱ የቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት
21 ሁለተኛይቱ የቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት
22 የመጀመሪያይቱ የቅዱስ ዮሐንስ መልእክት
23 ሁለተኛይቱ የቅዱስ ዮሐንስ መልእክት
24 ሦስተኛይቱ የቅዱስ ዮሐንስ መልእክት
25 የሐዋርያው የቅዱስ ያዕቆብ መልእክት
26 የሐዋርያው የቅዱስ ይሁዳ መልእክት
27 የዮሐንስ ራዕይ
28 መጽሐፈ ኪዳን ቀዳማዊ
29 መጽሐፈ ኪዳን ካልዕ
30 መጽሐፈ ሥርዓተ ጽዮን
31 መጽሐፈ አብጥሊስ
32 መጽሐፈ ግጽው
33 መጽሐፈ ትእዛዝ
34 መጽሐፈ ዲድስቅልያ
35 መጽሐፈ ቀሌምንጦስ
በድምሩ 81 [፹፩] ይሆናሉ።

እውነት ለሁሉ

27 Oct, 17:24


በእንተ ቅዱሳት ሥዕላት!
በዲያቆን ሸዋፈራው
ቅዱሳት ሥዕላት በመጽሐፍ ቅዱስ እና በቤተክርስቲያን ትምህርት!
ቅዱሳት ሥዕላት ጣኦታት ናቸው?
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!!

እውነት ለሁሉ

27 Oct, 10:33


"በመከራ ቀን ጥራኝ አድንኽማለኹ" መዝ 49:15
ዲያቆን ሸዋፈራው
………………………………………………
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

እውነት ለሁሉ

27 Oct, 06:14


ትናንት ማታ አንዱ ወዳጄ ደወለልኝ፣

"ተስፍሽ! ነገ በቅርቡ ወደተከፈተ አዲስ ቸርች እንሄዳለን "

"የምን ቸርች ነው?"

"የኮሪደር መንገዱን ለማሳለጥ የተከፈተ አዲስ ቸርች ነው"

"ስሙ ማነው?"

"የመኖሪያ መንገድ አዳሽ ቤተ ክርስቲያን"

ባሻዬ! በጠዋት ተነስቼ ወደ ጓደኛዬ ቤት አመራሁ። ቤቱ እንደደረስኩ ከባድ ጭቅጭቅ ሰማሁ። ጉዳዩ ጭቅጭቅ ሳይሆን ባልና ሚስት እየተፈራረቁ የቤት ሠራተኛዋን እየሰደቧት ነበር። ሠራተኛዋ ጥግ ላይ አንገቷን አቀርቅራ ቆማለች።

እኔም ግራ ገብቶኝ ጓደኛዬን ጠየቅሁት፣

"ምን ሆናችሁ ነው የምትጯጯሁት?"

""ይቺ የማትረባ ልጅ ነቻ!"

"ምን አደረገቾ?"

""በዚህ የኑሮ ውድነት በብዙ ሺህ ብር የተገዛውን ነቢይ ሱራፌል የፀለየበትን ዘይት ወጥ ሠራችበት"

"እና ወጡን በላችሁት?"

"አዎ! አሁን ቁርሳችንን የበላነው እሱን ነው"

እኔም የሚበቃኝን ያህል ከሳቅሁ በኋላ ጓደኛዬን ይዤው ወጣሁና አሁን የመኖሪያ መንገድ አዳሽ ቸርች ደርሰናል።

ባሻዬ! ቸርች ገብተን ከተቀመጥን በኋላ ዝማሬ ከተጀመረ ጀምሮ ይኸው ጓደኛዬ ተነስቶ እስካሁን እየዘለለ ነው። ምን ላድርገው?
@ከተስፍሽ

እውነት ለሁሉ

26 Oct, 21:04


“አንድ ምንም እውቀቱና ልምዱ የሌለው ሰው ዝም ብሎ መሬት ስለ ቆፈረ ብቻ ወርቅ አያገኝም፡፡ ከዚያ ይልቅ ምንም ረብሕና ጥቅም የሌለውን ድካም ያተርፋል እንጂ፡፡ ባስ ካለም የቆፈረው ጉድጓድ ተደርምሶበት ሕይወቱን ሊያጣ ይችላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት እንደሚነበብና እንዴት መረዳት እንዳለበት ያለወቀ ሰውም ይህን ሰው ይመስላል፡፡”

ቅዱስ ዮሐንስ  አፈወርቅ

እውነት ለሁሉ

25 Oct, 20:09


ብዙ ጊዜ ሙስሊም ወገኖቻችን ኢየሱስ ያህዌ አይደለም የሚል ሙግትን ያቀርባሉ

https://vm.tiktok.com/ZMhHLs2db/

እውነት ለሁሉ

25 Oct, 14:03


omg 🥺 ኧረ ጭካኔዉ
ክርስቲያን መሆን ሚፈልግም አንድ ሙስሊም በዚ ሁኔታ ነዉ እንዳይድን ሚደረገዉ በነፍሳቸዉ ላይ ወሰነዉ ጌታን የተቀበሉት በቤቱ ያፅናቸዉ አስልምና ግን እንደዚ ነዉ ነፃነትን ሚጨቁነዉ እዉነተኛዉ አምላክ ብዙ አምላክ ተብለዉ በነፃ ፍቃዳቸዉ ያመለኩትን በአለማችን ላይ ምንም ያላለ የነፃ ፍቃድ አምላክ ነዉ እስልምና በአለም ያለዉን የሚታየዉን ነፃ ፍቃድ አምላክ አዉነታ የተቃረነ ስለሆነ አላህ አምላክ አደለም ሊሆንም አይችል ሀኖም አያቅም

እውነት ለሁሉ

24 Oct, 06:54


"እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው"
ዮሐ5:39
ዲያቆን ሸዋፈራው አለነ
ክፍል አንድ
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

እውነት ለሁሉ

23 Oct, 04:49


ገጽ 262፣ ምዕራፍ 214፡ በዚህ ገጽና ምዕራፍ ላይ ደግሞ ‹‹30 የወርቅ ቁራጮች›› የሚል አገላለጽ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ነገር ግን በኢየሱስ ዘመን የፍልስጤም ገንዘብ የብር ቁራጮች ነበሩ፡፡
ማጠቃለያ፡- ከተሰጡት በርካታ ማስረጃዎች በመነሳት ሙስሊሞችም ሆኑ ክርስቲያኖች ይህ ‹የበርናባስ ወንጌል› የተሰኘው መጽሐፍ መለኮታዊ መነሻ እንደሌለው ሊያውቁ ይገባል፡፡ ሁሉም ማስረጃዎች የሚጠቁሙት ይህ መጽሐፍ በአውሮፓ ውስጥ ምናልባትም በመካከለኛው ዘመን ወቅት ክርስትናን ለማጥቃት ይውል ዘንድ በአንድ ግለሰብ የተቀነባበረ የፈጠራ ሥራ መሆኑን ነው፡፡ አንዳንድ ተመራማሪዎች ‹የበርናባስ ወንጌል› መጽሐፍ እስልምና በክርስቲያኖች አማካኝነት ከስፔን በመወገዱ ያዘነ፣ በዚህም ምክንያት ሙሐመድን ከኢየሱስ በላይ ለመሳል በሞከረ የስፔን ወይም የጣልያን ስረ መሠረት ባለው ግለሰብ የተጻፈ መጽሐፍ ሊሆን እንደሚችል ያስባሉ፡፡ ይህ ሊታመን የማይችል የፈጠራ ሥራ እውነትን በሚሹ ሰዎች በማስረጃ በተደገፈ መልኩ እየተጋለጠ ነው፣ እውነት ሁል ጊዜ ታሸንፋለችና!
____
[1]
የገላሲየስ አዋጅ
[2] Gnostic/ኖስቲክ የሚለው ቃል እውቀት ተብሎ ከሚተረጎም የግሪክ ቃል የመጣ ነው፡፡ ከግሪክ ዓለም ብዙ ሰዎች ድኅነት/መዳን የሚገኘው እውቀትን በማግኘት ነው ብለው ያምኑ ነበር፡፡ የግኖስቲክ አስተሳሰብ ወደ ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ አይነት መልክ ይገባ ሰለነበር ሐዋሪያት ይቃወሙት እንደ ነበር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተጠቅሷል፡፡ የኖስቲሲዝም አሳብ ብዙና የተለያየ ነበር፡፡ ዋና ዋና ትምህርታቸው የሚከተሉት ናቸው፡- 1. ሰው በእውቀት እግዚአብሔርን ያገኛል፡፡ 2. እውነተኛው ዓለም መንፈሳዊው ነው፡፡ 3. ሰው የሚድነው ከተፈጠረው ዓለም በመለያት ነው፡፡ አንዳንዶች ይህ የሚፈጸመው ሥጋን በመግዛትና በማድከም እንደሆነ በማስተማር ጋብቻን ከማድረግ እና ልዩ ልዩ ዓይነት ምግብን ከመመገብ መከልከልን አስተማሩ፡፡ 4. ከእግዚአብሔር ዘንድ አንድ ነገር መጥቷል፤ ቀጥሎም ሌላ ነገር መጣ፤ እንደዚሁም የተለያዩ ነገሮች እየመጡ በመጨረሻ ይህ የሚታየው ዓለም ተገኘ፡፡ ስለዚህ በዓለምና በእግዚአብሔር መካከል ብዙ ደረጃዎች ይገኛሉ፡፡ 5. ሰው የሚድነው በአዋቂዎች መካከል በሚደረግ ሥርዐትና ወግ ነው ይሉ ነበር፡፡ (የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት፣ 1972 ዓ.ም.)
[4] አርኪዮሎጂ፡- በድሮ ዘመን የነበሩትን ከተሞች፣ ቤቶች፣ ጽሑፎች፣ ሐውልቶች፣ ማለትም ቅርሶችን በመቆፈር ወይም በመፈለግ የጥንት ታሪኮችን የሚያጠና ጥበብ ነው፡፡

እውነት ለሁሉ

23 Oct, 04:49


ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር ከማረጉ አስቀድሞ ስለ መሞቱ ሌላም አስረጅ ጥቅስ አለ፡፡ በዚህ ክፍል ላይ ኢየሱስ እንዲህ ሲል ተጠቅሷል፡-
ሰላምም በኔ ላይ ነው፣ በተወለድሁ ቀን በምሞትበትም ቀን ሕያው ሆኜ በምቀሰቀስበትም ቀን፤ ሱረቱ መሪየም (19)፡33
So peace is on me the day I was born, the day that I die, and the day that I shall be raised up to life (again)!
ቅዱስ ቁርአን፡- ትርጉምና ማብራሪያ፣ (በኤ. ዩሱፍ አሊ)፣ የግርጌ ማስታወሻ ቁጥር 2485 እንዲህ ይላል፣ ‹‹…እርሱ (ኢየሱስ) አልሞተም ብለው የሚያምኑ ሰዎች ስለዚህ ጥቅስ አጥብቀው ማሰብ ይኖርባቸዋል፡፡›› ስለዚህ ጉዳይ አንስተው በርካታ ሙስሊሞች ምላሽ ለመስጠት ሲጥሩ፣ ኢየሱስ የሚሞተው ዳግመኛ ወደ ምድር ሲመለስ ነው ብለው ያስተምራሉ፡፡ ይበሉ እንጂ ይህ አስተምህሮ በቁርአን ውስጥ የለም!
እዚህ ላይ ሌላ ጠቃሚ ነጥብ እንመልከት፡፡ ጉዳዩ መጥምቁ ዮሐንስን ይመለከታል፡፡ ሙስሊሞች የሕያ እያሉ የሚጠሩት መጥምቁ ዮሐንስ በዚህ ‹የበርናባስ ወንጌል› በሚሰኘው መጽሐፍ ውስጥ ፈጽሞ ያልተጠቀሰ ሲሆን በቁርአንና በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ግን ታላቅ ስፍራ ተሰጥቶት እናገኛለን፡፡ የሕያ (መጥምቁ ዮሐንስ) ከኢየሱስ ፊት በመሄድ ስለ ኢየሱስ መምጣት ይመሰክር የነበረ አገልጋይ ነበር፡፡ የመጥምቁ ዮሐንስ ተቀዳሚ ተልኮ ደግሞ መሲሁ ኢየሱስ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ የተቀባ መሆኑን ማረጋገጥ ነበር፡፡ የበርናባስ ደራሲ ለምን መጥምቁ ዮሐንስን ከመጽሐፉ ፈፅሞ መደምሰስ እንደፈለገ አሁን ፍንትው ብሎ የሚታይ ይመስለናል፡፡ ይህ ደራሲ ሙሐመድን መሲህ ለማድረግ የመጥምቁ ዮሐንስን አገልግሎት በማስወገድ፣ ኢየሱስ የመጥምቁ ዮሐንስን ቦታ እንዲተካና ‹‹የመሲሁ›› ሙሐመድ ምስክር ማድረግ ነበረበት፡፡ ከእነዚህ ሁሉ ማስረጃዎች በኃላ ይህ መጽሐፍ ከቁርአን ትምህርቶች ጋር የሚጣረስ መሆኑን መገንዘብ ይኖርብናል ብለን እናምናለን!
ሐ. የተዛቡ ምልክዓ ምድራዊና ታሪካዊ ሁኔታዎች
ገጽ 22፣ ምዕራፍ 20፡ በዚህ ምዕራፍ ላይ ‹‹…ኢየሱስ በጀልባ በመሳፈር የእርሱ ከተማ ወደሆነችው ናዝሬት ተጓዘ›› የሚል ዐረፍተ ነገር እናነባለን፡፡ እውነታው ግን ናዝሬት በደረቅ መሬት ላይ የተከተመች ከተማ መሆኗ እንጂ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ እንደሚነግረን የወደብ ከተማ መሆኗ አይደለም፡፡
ገጽ 23፣ ምዕራፍ 21፡ እዚህ ላይ ደግሞ ‹‹ወደ ቅፍርናሆም በእግሩ ተጓዘ፡፡›› የሚል ዐረፍተ ነገር እናነባለን፡፡ ነገር ግን ቅፍርናሆም በገሊላ ባሕር የምትገኝ የወደብ ከተማ መሆንዋን ልብ ይሏል፡፡
ገጽ 116፣ ምዕራፍ 92፡ በዚህ ገጽና ምዕራፍ ላይ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሲና ተራራ ከወጣ በኃላ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ቀረበ ተብሎ ተጽፏል፡፡ ነገር ግን የሲና ተራራ በስተ ግብጽ በኩል ባለው የእሥራኤል ክፍል የሚገኝ ሲሆን፣ የዮርዳኖስ ወንዝ ደግሞ በስተ ዮርዳኖስ በኩል ባለው የእሥራኤል ክፍል የሚገኝ ወንዝ ነው፡፡ እነዚህ ሁለቱ ቦታዎች በጣም የሚራራቁ ቦታዎች ናቸው!
ገጽ 217፣ ምዕራፍ 169፡ በዚህ ምዕራፍ ላይ፣ ‹‹ሁሉ ነገር ፍሬ አዝሎ በሚታይበት የበጋ ወራት ይህ ስፍራ እንዴት ውብ ነው፡፡›› የሚል አገላለጽ ሰፍሮ እናነባለን፡፡ እርግጥ ነው፣ ይህ አገላለጽ እንደ አውሮፓ ባሉ አካባቢዎች ላይ ሲነበብ ትርጉም ይኖረዋል፡፡ መሬቱ ክው በሚልበትና ከሚባላው ፀሀይ የተነሳ ምድር ፍሬዋን በምትከለክልበት በፍልስጤም የበጋ ወራት አውድ ሲነበብ ግን አባባሉ ተቃራኒ ትርጉም ከመስጠት ውጪ ሊላ አማራጭ ሊኖረው አይችልም፡፡
ገጽ 4፣ ምዕራፍ 3፡ እዚህ ምዕራፍ ላይ ደግሞ፣ ‹‹አናኒያና ሰጲራ ካህናት በሆኑበት ዘመንና ፒላጦስ ደግሞ ገዢ በሆነበት ዘመን ኢየሱስ ተወለደ›› ሲል ያስነብበናል፡፡ ከታሪክ የምንረዳው ደግሞ፣ ፒላጦስ ከ26-27 ዓ.ም. በፊት ገዢ እንዳልነበረ ነው፡፡ እዚህ ላይ፣ ‹‹የበርናባስ መጽሐፍ›› ፒላጦስን ባልኖረበት ዘመን ገዢ እንዳደረገው እንመለከታለን፡፡
ገጽ 11፣ ምዕራፍ 12፡ በዚህ ገጽና ምዕራፍ ላይ ደግሞ ‹‹ወደ ቤቱም ሰገነት ላይ ወጣ›› የሚል ዐረፍተ ነገር እናነባለን፡፡ ይሁንና ይህ አባባል፣ አውሮፓ ውስጥ ንግግሮች በረጃጅም ሰገነቶች ላይ የሚሰጡበትን የ15ኛውንና 16ኛውን መካከለኛው ክፍለ ዘመን የሚገልጥ እንጂ በምኩራቦቻቸው ውስጥ ስብከቶች የሚሰጡባቸውን የአይሁድና ፍልስጤማውያንን ታሪክ ፈጽሞ አይወክልም፡፡
ገጽ 19፣ ምዕራፍ 18፡ 000 የሚሆኑ ነቢያት ኤልዛቤል በተባለች ሴት መታረዳቸው ተጠቅሷል፡፡ ሆኖም ይህ ጉዳይ በቅዱሳት መጻሕፍትም ሆነ በታሪክ ድርሳናት ላይ ፈጽሞ ተጠቅሶ አናነብም፡፡ በዚህ ክፍል ላይ ደግሞ፣ 10
ገጽ 41፣ ምዕራፍ 32፡ በዚህ ክፍል ላይ መጽሐፉ የበአል ጣኦት አምልኮ በዓለም ገጽ ሁሉ ተንሰራፍቶ እንደ ነበር ያስነብበናል፡፡ ሆኖም ይህንን የሚያረጋግጥ ምንም አይነት የአርኪዮሎጂ [4] ጥናት ማስረጃ አልተገኘም፡፡
ገጽ 82፣ ምዕራፍ 65፡ በዚህ ገጽና ምዕራፍ ላይ ደግሞ የመዋኛ ገንዳን ለመጥቀስ ፕሮባቲካ (probatica) የተሰኘ ቃል ጥቅም ላይ ውሎ እናገኛለን፡፡ ሆኖም ይህ ቃል የግሪክ ሆኖ ከኢየሩሳሌም ደጆች መካከል አንዱ ለሆነውን ‹‹የበጎች በር›› ስያሜ የዋለ ነው፡፡
ገጽ 115፣ ምዕራፍ 91፡ ል፡፡ እንዲህ አይነቱ ነገር ከፍተኛ ግነት ከመሆኑ በተጨማሪ በሮም የታሪክ መዛግብት ላይ የማይገኝ ታሪክም ጭምር ነው፡፡ በዚህ ክፍል ላይ 600000 የሚደርሱ የሮም ወታደሮች ሚዝፔህ (Mizpeh) በተሰኘች ትንሽ መንደር ውስጥ ተከማችተው እንደ ነበረ ተገልጸ
ገጽ 130፣ ምዕራፍ 103፡ ‹‹መርከበኛ›› እና ‹‹መርከብ›› የሚሉት ቃላት በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የተጠቀሱ ሲሆን እነዚህ ቃላት ኢየሱስ አገልግሎቱን ይፈጽምበት በነበረበት ዘመን በፍልስጤም አካባቢ የተለመዱ ቃላት አልነበሩም፡፡ እነዚህ ቃላት ይበልጥ የመካከለኛውን ዘመን የስፔን እና የጣልያን አካባቢዎች የሚገልጹ ናቸው፡፡
ገጽ 185፣ ምዕራፍ 145፡ በዚህ ምዕራፍ ላይ በነቢል፡፡ እውነታው ግን ፈሪሳውያን ከክርስቶስ ልደት በፊት እስከ 200 ዓመት ዓለም፣ የአይሁድ መቃቢያን ዘመን ድረስ ያልነበሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ኤሊያስ ደግሞ ከዚህ ዘመን 700 አመት በፊት፣ ከክርስቶስ ልደት በፊት በ900 ዓ.ዓ. የኖረ ነቢይ ነበር፡፡ ዩ ኤልያስ ዘመን 17000 የሚሆኑ ፈሪሳውያን መኖራቸው ተገልጸ
ገጽ 196፣ ምዕራፍ 152፡ እዚህ ምዕራፍ ላይ ደግሞ ‹‹ወይን ከመሞላታቸው በፊት ለመታጠብ እንደተደረደሩ፣ ከእንጨት እንደተሰሩ የአልኮል መጠጥ በርሜሎች፣ ወታደሮች በዝግታ ሲያልፉ…›› የሚል አገላለጽ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡ ሆኖም ግን በኢየሱስ የአገልግሎት ዘመን ከእንጨት የተሰሩ በርሜሎች የተለመዱ አልነበሩም፡፡ የዛን ዘመን ብቻ ሳይሆን አሁን ድረስ በእነዚህ ስፍራዎች የወይን ማስቀመጫዎች ከእንስሳ ቆዳ እንጂ ከእንጨት በርሜሎች አይሰሩም፡፡ ከእንጨት የተሰሩ የወይን በርሜሎች፣ በወቅቱ ወደ ሌላ የዓለም ክፍል ሳይቀር ይላኩ የነበረበትን የመካከለኛ ዘመን አውሮፓ ታሪክን የሚገልጽ ነው፡፡

እውነት ለሁሉ

23 Oct, 04:49


ገጽ 51፣ ምዕራፍ 39፡ ይህ ክፍል ደግሞ አዳምና ሔዋን የፖም ፍሬንና በቆሎን እንዳይበሉ እንደተከለከሉ ያስነብበናል፡፡ ነገር ግን ቁርአኑ የሚከተለውን ይላል፡-
አዳም ሆይ! አንተ ከነሚስትህ በገነት ተቀመጥ፤ ከእርሷም በፈለጋችሁት ስፍራ በሰፊው ተመገቡ፤ ግን ይህችን ዛፍአትቅረቡ፤ ከበደለኞች ትሆናላችሁና አልንም፡፡ ሱረቱ አል-በቀራህ (2)፡35
O Adam! Dwell thou and thy wife in the Garden; and eat of the bountiful things therein as (where and when) ye will: but approach not this tree, or ye run into harm and transgression.
‹‹ፖም›› እንዳይበላ ከታዘዙት የዛፍ ፍሬዎች መካከል አንዱ ሊሆን ይችል ይሆናል፣ የእህል ዘር የሆነው ‹በቆሎ› ዛፍ ላይ አለመብቀሉ ግን እንግዳ ነገር ሊሆን አይችልም!
ገጽ 57፣ ምዕራፍ 44፡ እዚህ ምዕራፍ ላይ ደግሞ ለይስሃቅ ዘር የተገባው የተስፋ ቃል ወይም ቃል ኪዳን ተሰርዟል የሚል እናነባለን፡፡ መጽሐፉ ይህን ቢልም ቁርአን እግዚአብሔር ቃል ኪዳንን ከእስማኤልና ከዘሩ ጋር ስለመገባቱ ምንም የሚለው ነገር የለም፡፡ እንዲህ አይነቱ የተስፋ ቃል ወይም ቃል ኪዳን ከይስሃቅ ማለትም ከእሥራኤል (ከያዕቆብ) እና ዘሩ ጋር በተያያዘ ግን በቁርአን ውስጥ ተጠቅሶ እናነባለን፡፡ የሚከተለውን የቁርአን ጥቅስ እናንብ፡-
የእሥራኤል ልጆች ሆይ! ያችን በእናንተ ላይ የለገስኳትን ጸጋዬን አስታውሱ፤ በቃል ኪዳኔም ሙሉ፤ በቃል ኪዳናችሁ እሞላለሁና፤ እኔንም ብቻ ፍሩ፡፡ ሱረቱ አል-በቀራህ (2)፡40
O Children of Israel! Call to mind the (special) favor which I bestowed upon you, and fulfill your covenant with Me as I fulfill My Covenant with you, and fear none but Me.
ገጽ 132፣ ምዕራፍ 105፡ ይህ ክፍል ስለ ‹‹ዘጠኝ›› ሰማያት ሲጠቅስ ቁርአን ግን ስለ ሰባት ሰማያት ብቻ ነው የሚያወራው፡፡
እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለናንተ የፈጠረ ነው፤ ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው፤ እርሱም በነገሩ ሁሉ አዋቂ ነው፡፡ ሱረቱ አል-በቀራህ (2)፡29
Moreover His design comprehended the heavens, for He gave order and perfection to the seven firmaments;…
ገጽ 134፣ ምዕራፍ 106፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ጀሀነም /ገሃነም (ሲኦል)/ ሊቋቋሙት በማይችሉት የበረዶ ግግር ስፍራ ተመስሏል፡፡ በርካታዎቹ የቁርአን ጥቅሶች ግን ይህን ስፍራ በሚቃጠል ነበልባልና በተንቀለቀለ (በፈላ) ውሃ ይመስሉታል፡፡
ገጽ 141፣ ምዕራፍ 112፡ ይህ ክፍል ደግሞ ኢየሱስ እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ወደ ሰማይ እንደማያርግ መናገሩን ያስነብበናል፡፡ የሚከተለው የቁርአን ማስረጃ ግን በተቃራኒው እንዲህ ይላል፡
አላህም ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ ዒሳ [ኢየሱስ] ሆይ! እኔ ወዳጂህ ወደ እኔም አንሺህ ነኝ፤ ከነዚያም ከካዱት ሰዎች አጥሪህ ነኝ፤ እነዚያንም የተከተሉህን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ከእነዚያ ከካዱት በላይ አድራጊ ነኝ፤ ከዚያም መመለሻችሁ ወደኔ ነዉ፤ በርሱ ትለያዩበትም በነበራችሁት ነገር በመካከላችሁ እፈርዳለሁ፡፡ ሱረቱ አሊ-ዒምራን (3)፡55
Behold! God said: “O Jesus! I will take thee and raise thee to Myself….”
ይልቁንስ አላህ ወደርሱ አነሳው፤ አላህም አሸናፊ ጥበበኛ ነው፡፡ ሱረቱ አል-ኒሳእ (4)፡158
Nay, God raised him up unto Himself; and God is exalted in power, Wise.
ገጽ 156፣ ምዕራፍ 124፡ እዚህ ክፍል ላይ፣ ዛቡር [መዝሙረ ል፡፡ ዳዊት] የተሰጠበት ምክንያት ቶራ [የሙሴ መጻሕፍት] ስለተበረዘ መሆኑና ኤንጅል [አዲስ ኪዳን] የተሰጠው ደግሞ የዛቡር መጽሐፍ በመበረዙ ምክንያት እንደሆነ ተገልጸ
ይሁን እንጂ ይህ አይነቱ የምክንያት ዝርዝር በቁርአኑ ውስጥ አልተገለጸም፡፡ በታቃራኒው፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ቅዱሳት መጻሕፍት ለሰው ዘር ምሪቶችና ብርሃኖች እንደሆኑ ይመሰክርላቸዋል እንጂ፡፡ እነዚህ ቅዱሳት መጻሕፍት ተበርዘው ቢሆን ኖሮ ቁርአን ስለ መጽሐፍ ቅዱስ የሚከተለውን ባላለ ነበር፡-
እነሱም ተውራትንና ኢንጂልን ከጌታቸው ወደነሱ የተወረደውን መጽሐፍ ባቋቋሙ (በሰሩበት) ኖሮ ከበላያቸውና ከእግሮቻቸው ስር በተመገቡ ነበር፤ …[በሙሴ መጻሕፍት፣ በወንጌል እና ከጌታቸው ወደ እነሱ በወረዱ መገለጦች ጸንተው ቢኖሩ ኖሮ ደስታን በሁሉ የሕይወት አቅጣጫ በተለማመዱ ነበር፡፡] ሱረቱ አል-ማኢዳህ (5)፡66
If only they had stood fast by the Law, the Gospel, and all the revelation that was sent to them from their Lord, they would have enjoyed happiness from every side.
እላንተ ያመናችሁ ሆይ! በአላህና በመልክተኛው፣ በዚያም በመልክተኛው፣ ላይ ባወረደዉ መጽሐፍ፣ በዚያምከበፊቱ ባወረደው መጽሐፍ እመኑ [ከቁርአን በፊት በወረዱት ቅዱሳት መጻሕፍት ማለትም በሙሴ መጻሕፍት፣ በነቢያት መጻሕፍት እና በወንጌል እመኑ]፤ በአላህና በመላእክቱም በመጽሐፎቹም፣ በመልክተኞቹም በመጨረሻዉም ቀን የካደ ሰው (ከዉነት) የራቀን መሳሳት በእርግጥ ተሳሳተ፡፡ ሱረቱ አል-ኒሳእ (4)፡136
O ye who believe! Believe in God and His apostle, and the scripture which He hath sent to His apostle and the scripture which He sent to them before him. Any who denieth God, His angels, His Books, His Apostles, and the Day of Judgment hath gone far, far astray
ገጽ 273፣ምዕራፍ 221፡ በዚህ ክፍል ላይ ደግሞ ኢየሱስ ‹‹አልሞትኩም፡፡›› ብሎ ሲናገር ተጠቅሷል፡፡ ምንም እንኳ በርካታ ሙስሊሞች የኢየሱስን ሞት ቢክዱም ቁርአን ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ምንም ግልጽ ማስረጃ አይሰጥም፡፡ ከዚህ በተቃራኒ ግን፣ ቁርአኑ ኢየሱስ ወደ እግዚአብሔር ከማረጉ በፊት እንደ ሞተ ጠንካራ ማስረጃ ይሰጣል፡፡ የሚከተለውን የቁርአን ማስረጃ እንመልከት፡-
አላህም ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ ዒሳ [ኢያሱስ] ሆይ! እኔ ወዳጂህ ወደ እኔም አንሺህ ነኝ፤ ከነዚያም ከካዱት ሰዎች አጥሪህ ነኝ፤ እነዚያንም የተከተሉህን እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ ከለዚያ ከካዱት በላይ አድራጊ ነኝ፤ ከዚያም መመለሻችሁ ወደኔ ነዉ፤ በርሱ ትለያዩበትም በነበራችሁት ነገር በመካከላችሁ እፈርዳለሁ፡፡ ሱረቱ አሊ-ዒምራን (3)፡55
Behold! God said, “O Jesus, I will take thee and raise thee to Myself….”

‹‹እኔ ወሳጅህ ወደ እኔም አንሺህ ነኝ›› የሚለው አባባል አረብኛ አገላለጽ ታዋፊቅ/tawaffik ሲሆን ትርጓሜውም ‹‹እንድትሞት አደርግሃልሁ፡፡›› ማለት ነው፡፡ ይህ አባባል በሱረቱ-አል መኢዳህ (5)፡117 አንቀጽ ውስጥ ጥቅም ላይ የዋለ ሲሆን በዚህም ስፍራ ላይ ያለው የቃል በቃል አረብኛ አገላለጽ ትርጉም፣ ‹‹እንድሞት ባደረግኸኝ ጊዜ›› ማለት ነው፡፡

እውነት ለሁሉ

23 Oct, 04:49


Maedot:
‹የበርናባስ ወንጌል› እውነተኛ ወንጌል ነውን?/ሙስሊሞች ባትዘባርቁ መልካም ነው/
አዲስ ኪዳን ዋናው የወንጌል ቅጂ አይደለም የሚሉ አንዳንድ ሙስሊሞች ‹ትክክለኛ› ነው የሚሉትን ለማግኘት ውጤት አልባ ልፋት ለፍተዋል፡፡ በመጨረሻ ላይ እነዚህ ፈላጊዎች ሊያደርጉት የቻሉት ‹ትልቁ ነገር› ቢኖር ‹የበርናባስ ወንጌል› የሚባል መጽሐፍን ለዚህ ጥያቄያቸው እንደ መልስ ማቅረብ መቻላቸው ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ ተጻፈ የሚባለው በሐዋሪያው ጳውሎስ የመጀመሪያው የሚሽነሪ ጉዞ ወቅት አብሮት በነበረው አማኝ ‹‹በርናባስ ነው›› (የሐዋሪያት ሥራ 13፡1-4)፡፡ አንድ ዘመናዊና ጥልቅ ጥናት ስለዚህ ‹የበርናባስ ወንጌል› ስለ ተሰኘው መጽሐፍ የሚከተለውን ያስነብበናል፡-
በርካታ ቀደምት ጸሐፍት በሥራዎቻቸው ‹የበርናባስ ወንጌል› የሚል ርዕስ ጠቅሰዋል፡፡ ይህ ርዕስ በገላሲየስ አዋጅ(500ዓ.ዓ.) [1] ‹‹Decree of Galasius›› ውስጥም ተጠቅሶ እናገኘዋለን፡፡ ነገር ግን ርዕሱን ከመጥቀስ ውጪ ስለ ሥራው ይዘትም ሆነ ገጸ-ባሕሪያት በነዚህ ማጣቀሻ መጻሕፍ ውስጥ ምንም የተባለ ነገር አይገኝም፡፡ ይሁንና፣ ‹የበርናባስ ወንጌል› የሚል ርዕስን በላዩ የያዘ በጣሊያንኛ ቋንቋ የተጻፈ ረቂቅ በአሁኑ ሰአት ይገኛል፡፡ ረቂቁ ጠንካራ የኖስቲሲዝም/Gnosticicm [2] አሳብን የሚያንጸባርቅና ከሙስሊም አቋም አንጻር የተጻፈ ነው፡፡ መጽሐፉ በ 1907 በሎንስዳል እና በላውራ (ኤም ሮበርትስ) ራግ አርትኦት ተደርጎበታል፡፡ መጽሐፉ፣ እንደ ብዙዎቹ የመካከለኛ ዘመን የቤተ-ክርስቲያን አባቶች ጽሑፎች/ patrisitic እና መቃቢያን/apocrypha [3]፣ እጅጉን አሳባዊ ነው፡፡ ግልጽና ጠንካራ ሥነ-ምግባራዊ ይዘት ቢኖረውም ሥራው በታሪካዊ እዉነታዎች ላይ ያልተመሰረተና ልብ-ወለዳዊ ነው፡፡ ኢንሳይክሎፒዲያ አሜሪካና የ1976 ህትመት፣ ገጽ 247
በመጽሐፉ አወዛጋቢ ባሕሪ ምክንያት፣ ለ ‹የበርናባስ ወንጌል› መጽሐፍ ትኩረት የሚሰጡት በጣም ጥቂት ሙስሊሞች ብቻ ናቸው፡፡ እነዚህም ቢሆኑ መጽሐፍ ቅዱስንና ክርስትናን ስሜታዊ በሆነና ማስረጃ በጎደለው መንገድ ለማጥቃት በብርቱ የሚመኙቱ ናቸው፡፡ በእስልምና እውቀት የገፉና የፍልስጤምን መልክአ ምድርና ታሪክ ጠንቅቀው የሚያውቁ ሁሉ ለዚህ መጽሐፍ መለኮታዊ መሰረት መስጠት በእስልምና ላይ ግልጽና አሳፋሪ ድርጊት መፈጸም እንደሆነ ይረዳሉ፡፡ ‹የበርናባስ ወንጌል› መጽሐፍ፣ ቁርአንንና በኢየሱስ ዘመን የነበረውን የፍልስጤም ታሪካዊ ዳራ በጉልህ ይጻረራል፡፡ እነዚህ ልዩነቶች ከዚህ በታች በየፈረጁ ተዳሰዋል፡-
ሀ. የመሲሁ ማንነት
ከበርናባስ መጽሐፍ (ህትመት 1907) ዋነኛ አላማዎች መካከል አንዱ የመሲህነትን መዕረግ (ስያሜ) ከኢየሱስ ወደ ነቢዩ ሙሐመድ ማሻገር ነው፡፡ ሆኖም ይህ ሙከራ በውስጣዊም ሆነ ውጪያዊ ማስረጃዎች አንጻር የሚያመጣው ግጭት ግልጽ ነው፡፡
የሚከተሉት መረጃዎች የመጽሐፉ ደራሲ ‹‹መሲህ›› የሚለውን ስያሜ ከኢየሱስ ላይ ለማንሳት ላደረገው ጥረት አስረጂዎች ናቸው፡፡
ገጽ 122፣ ምዕራፍ 96፡ ኢየሱስ እኔ መሲህ አይደለሁም አለ
ገጽ 123፣ ምዕራፍ 97፡ ሙሐመድ መሲሁ ነው
ገጽ 182፣ ምዕራፍ 142፡ መሲሁ ከዳዊት ወይም ከይስሃቅ ዘር ግንድ አይደለም
ከላይ ከተገለጸው መረጃ በተቃራኒው ቁርአን አል-መሲህ (መሲሁ) የሚለውን ማዕረግ ከማሪያም ልጅ ከኢየሱስ በቀር ለማንም አለመስጡን በግልፅ ያስነብበናል፡፡ መሲህ የሚለው ልዩ ስያሜ በቁርአን ውስጥ ነቢዩ ሙሐመድን ጨምሮ ለማናቸውም ሌሎች ነቢያት አልተሰጠም፡፡ የሚከተሉትን የቁርአን ጥቅሶች እንመልከት፡-
እላንተ የመጽሐፉ ሰዎች ሆይ! በሃይማኖታችሁ ወሰንን አትለፉ፤ በአላህም ላይ እውነትን እንጅ አትናገሩ፤ የመርየም[የማሪያም] ልጅ አልመሲሕ [መሲህ] ዒሳ [ኢየሱስ] የአላህ መልክተኛ ወደ መርየም የጣላት (የኹን) ቃሉም ከርሱ የኾነ መንፈስም ብቻ ነዉ፤ …ሱረቱ አል-ኒሳእ (4)፡171
Christ Jesus (Al-Masih Isa) the son of Mary was (no more than) an apostle of God, and His Word, which He bestowed on Mary, and a Spirit proceeding from Him.
መላእክት ያሉትን (አስታውስ)፡- መርየም [ማሪያም] ሆይ! አላህ ከእርሱ በሆነው ቃል ስሙ አልመሲህ [መሲህ] ዒሳ [ኢየሱስ] የመሪየም ልጅ በዚህ ዓለምና በመጨረሻውም ዓለም የተከበረ ከባለሟሎችም በሆነ (ልጅ) ያበስርሻል፡፡ ሱረቱ አሊ-ዒምራን (3)፡45
Behold! The angels said: “O Mary, God giveth thee glad tidings of a Word from Him; his name will be Christ Jesus (Al-Masih Isa), the son of Mary, held in honor in this world and the hereafter.”
ሙስሊሞች ልክ መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚለው ኢየሱስ ከአብርሃም፣ ይስሃቅና ያዕቆብ ዘር፣ ከነቢዩ ዳዊት ሥር የተገኘ አይሁዳዊ መሲህ እንደሆነ ያምናሉ፡፡ ‹የበርናባስ ወንጌል› ከዚህ እውነት በተቃራኒው መሲሁ ከዳዊት ወይም ከይስሃቅ ዘር ግንድ አልተገኘም ማለቱ በግልጽ ከሙስሊም እምነት ጋር የሚቃረን መሆኑን ያሳየናል፡፡
የበርናባስ መጽሐፍ ደራሲ በመጽሐፉ ዳር እስከ ዳር ለኢየሱስ፣ ክርስቶስ የሚል ስያሜ ሰጥቶ ሲያበቃ መልሶ ኢየሱስ መሲህ አይደለም ብሎ ይከራከራል! ክርስቶስ ማለት መሲህ ማለት መሆኑን ልብ ይሏል፡፡
ለ. የተዛቡ ጥቅሶችና የባህሎች
ገጽ 5፣ ምዕራፍ 3፡ በዚህ ምዕራፍ ውስጥ፣ ማርያም ያለምንም ስቃይ ኢየሱስን እንደ ወለደች ተጠቅሷል፡፡ ቁርአን ግን በተቃራኒው የሚከተለውን ያስነብበናል፡-
ወዲየውኑም አረገዘችው፤ በርሱም (በሆድዋ ይዛው) ወደ ሩቅ ስፍራ ገለል አለች፤ ምጡም ወደ ዘንባባዬቱ ግንድ አስጠጋት፣ ዋ ምኞቴ! ምነው ከዚህ በፊት በሞትኩ፤ ተረስቼም የቀረሁ በሆንኩ አለች፡፡ ሱረቱ መሪየም (19)፡22-23
So she conceived him (Jesus), and she retired with him to a remote place. And the pains of childbirth drove her to the trunk of a palm-tree: She cried (in her anguish): “Ah! Would that I had died before this!”
ገጽ 26፣ ምዕራፍ 23፡ እዚህ ክፍል ላይ ደግሞ ግዝረት በአዳም እንደ ተጀመረ ይናገራል፡፡ ነገር ግን የእስማኤላውያን ባሕልም ሆነ መጽሐፍ ቅዱስ ይህ ስርአት በአብርሃም እና እስማኤል ማህበረሰብ ወቅት እንደ ተጀመረ ይናገራሉ፡፡
ገጽ 46፣ ምዕራፍ 35፡ ይህ ምዕራፍ፣ የሰው እንብርት ከሰይጣን አክታ መሰራቱን ያስነብበናል፡፡ በገጽ 50፣ ምዕራፍ 39 ላይ ደግሞ ‹‹የበርናባስ ወንጌል›› ደራሲ ውሻ ከሰይጣን አክታ ነው የተፈጠረው ይለናል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም ሆነ ቁርአን ሰይጣን በሰው ልጅ አፈጣጠር ውስጥ (የሰውን እንብርት ጨምሮ) ድርሻ እንደ ነበረው የሚጠቁሙን ነገር የላቸውም፡፡ በተጨማሪም፣ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔር በፍጥረት ሥራው ውስጥ የሰይጣንን እርዳታ እንደማይሻ የበርካታ ሙስሊሞች እምነት እንደሆነ እርግጠኞች ነን!

እውነት ለሁሉ

22 Oct, 16:25


John Chrysostom Roman 8:26



The Spirit is always there to help us and to do his part…. Since we are ignorant of much that is profitable for us and we ask for things which are not profitable, the gift of prayer used to come into one person in the church, and he would be the person set aside to ask God for the things which would benefit them all. Here the word Spirit is the name which Paul gives to the kind of grace and to the soul who receives it and intercedes with God on our behalf. The one who was counted worthy of such a grace as this would stand with great attention, and with many mental groanings he would fall before God, asking the things which were profitable for all. Nowadays, the deacon is a symbol of this, when he offers up the prayers for the people.

እውነት ለሁሉ

22 Oct, 04:39


🖋ውይይት

ወንድም እፎይ
ወንድም ጄምዲ
ወንድም ክርስቲያን
ከሙስሊም ወገኖቻችን ጋር 🖋

ከእስልምና የወጣ ይገደላል🙆

እኔ አንተን ባገኝህ እገልሃለሁ አለው 👈

ሌሎችም እርሶችንም የተዳሰሰበት ውይይት
ይደመጥ

እውነት ለሁሉ

20 Oct, 15:51


"የመሰናከያ ዐለት አኖራለው" ሮሜ9:31
ዲያቆን ሸዋፈራው
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

እውነት ለሁሉ

20 Oct, 04:54


ዛሬ ከተነበበዉ ወንጌል

ማቴዎስ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ በሰንበት ቀን በእርሻ መካከል አለፈ፤ ደቀ መዛሙርቱም ተራቡና እሸት ይቀጥፉ ይበሉም ጀመር።
² ፈሪሳውያንም አይተው፦ እነሆ፥ ደቀ መዛሙርትህ በሰንበት ማድረግ ያልተፈቀደውን ያደርጋሉ አሉት።
³-⁴ እርሱ ግን እንዲህ አላቸው፦ ዳዊትና ከእርሱ ጋር የነበሩት በተራቡ ጊዜ፥ እርሱ ያደረገውን፥ ወደ እግዚአብሔር ቤት እንደ ገባ ካህናትም ብቻ እንጂ እርሱና ከእርሱ ጋር የነበሩት ሊበሉት ያልተፈቀደውን የመሥዋዕቱን ኅብስት እንደ በላ አላነበባችሁምን?
⁵ ካህናትም በሰንበት በመቅደስ ሰንበትን እንዲያረክሱ ኃጢአትም እንዳይሆንባቸው በሕጉ አላነበባችሁምን?
⁶ ነገር ግን እላችኋለሁ፥ ከመቅደስ የሚበልጥ ከዚህ አለ።
⁷ ምሕረትን እወዳለሁ መሥዋዕትንም አይደለም ያለው ምን እንደሆነ ብታውቁስ ኃጢአት የሌለባቸውን ባልኰነናችሁም ነበር።
⁸ የሰው ልጅ የሰንበት ጌታ ነውና።
⁹ ከዚያም አልፎ ወደ ምኩራባቸው ገባ።
¹⁰ እነሆም፥ እጁ የሰለለች ሰው ነበረ፤ ይከሱትም ዘንድ። በሰንበት መፈወስ ተፈቅዶአልን? ብለው ጠየቁት።
¹¹ እርሱ ግን፦ ከእናንተ አንድ በግ ያለው በሰንበት በጉድጓድ ቢወድቅበት፥ ይዞ የማያወጣው ሰው ማን ነው?
¹² እንግዲህ ሰው ከበግ ይልቅ እንደምን አይበልጥም! ስለዚህ በሰንበት መልካም መሥራት ተፈቅዶአል አላቸው።
¹³ ከዚያም በኋላ ሰውየውን፦ እጅህን ዘርጋ አለው። ዘረጋትም፥ እንደ ሁለተኛይቱም ደህና ሆነች።
¹⁴ ፈሪሳውያን ግን ወጥተው እንዴት አድርገው እንዲያጠፉት ተማከሩበት።
በወልድ ያመነ የዘላለም ሕይወት አለዉ ።

መልካም ዕለተ ሰንበት 🤗

እውነት ለሁሉ

19 Oct, 19:49


"ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል" ሉቃ1:48
ዲያቆን ሸዋፈራው አለነ
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!

እውነት ለሁሉ

17 Oct, 16:17


"ከሞተ አንበሳ ያልሞተ ውሻ ይሻላል" ምሳ 9:6

Share Share Share

………………………………………………

ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ወንጌል ይማሩ...!
👇👇👇👇👇👇👇
👉 https://t.me/orthodoxawitewahdo  👈
👆👆👆👆👆👆👆
ሊንኩን ተጭነው ያንብቡ
👇👇👇👇👇👇👇
http://telegra.ph/ከሞተ-አንበሳ-ያልሞተ-ውሻ-ይሻላል-11-29

እውነት ለሁሉ

15 Oct, 20:20


እያረፋችሁ ስሙት
#ኢሳ #ኢየሱስ_ነው ማለት ድሮ ቀረ

ወንድማችን ክበርልን
@OT_Christian 😍

እውነት ለሁሉ

15 Oct, 15:41


ዮሐንስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³³ ኢየሱስም፦ ገና ጥቂት ጊዜ ከእናንተ ጋር እቆያለሁ ወደ ላከኝም እሄዳለሁ።
³⁴ ትፈልጉኛላችሁ አታገኙኝምም፤ እኔም ወዳለሁበት እናንተ ልትመጡ አትችሉም አለ።
ኢየሱስ እንደማይዙት ብለዉ ሚያነሱት
ዋና ነጥባቸዉ እሄ ነዉ እሄ ጥቅስ ክርስቶስ እንዳልተሰቀለ አሰረጂ አርገዉ ብዙ መስሊሞች ያወራሉ ግን ስህተት ነዉ
(ማር10:45) (ሉቃ 24:6-7) እንዲሁም ጴጥሮስን የሰዉ ለጅ ማን ብለዉ ይሉታል ብሎ በጠየቀበት ላይ የሕያዉ የእግዘአብሔር ልጅ ነህ በሚል ትምህርቱ ላይ ቤተክርሰተያንን መስርቶ አንደሚሰቀል እንደሚነሳ ከተናገራቸወ በኃላ ጴጥሮስ በሀዘኔታ አትሙት ሲለዉ ጊዜ ጌታም እንዲ ብሎ ነበረ
“እርሱ ግን ዘወር ብሎ ጴጥሮስን፦ ወደ ኋላዬ ሂድ፥ አንተ ሰይጣን፤ የሰውን እንጂ የእግዚአብሔርን አታስብምና ዕንቅፋት ሆነህብኛል አለው።”
— ማቴዎስ 16፥23 እንግዲ ኢየሱስ ጴጥሮስ በኃዘኔታ አትሙት ብሎ ቢያስብ ያ ሀሳቡ የሰይጣን እንደሆነ አንደዉም ሂድ እስከማለት ድረስ የተናገረዉን ስናስብ የክርስቶስ ሀሳብም አላማም መሞትን አርጎ እንደመጣ በደብ ያስረግጣል

(በዩሀ7:33_34 የሀ8:21_22) እንዲሁም በሌሎች ክፍሎች ላይ ጌታን እንደማያገኙት እሱ ወዳለበት ቦታ እንደማይመጡ የተናገረበተ አነቀፅ አለ

እዚህ ጋ ሚያነሱት ጥያቄ አለ እሱም አታገኙኝም ብሏል እንዴት አገኙት ኢየሱስ እንዴት ይሰቀላል ይላሉ ከጅምሩም የሙግት ሀሳባቸዉ ስህተት ምክንያቱም ጌታ እንደማያገኙት የተናገረዉ በቤተ መቅደስ ለሁሉም ነዉ እንጂ የሚሰቅሉትን ለአይሁዶች ብቻ አደለም
“ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር ዩሀ8:20(ዩሀ7:28) ከዚህ ተነስተን የሙግት ነጥባቸዉ ሊደግፋቸዉ ሚችለዉ ለሚሰቅሉት ብቻ የተናገረ ቢሆን ነበር ግን ለሁሉም ለሕዝብ በቤተመቅደሰ ነዉ የተናገዉ ስለዚህ የሚሰቅሉት ለአይሁድ ብቻ ሳይሆን ለሕዝቡ እስራኤልም ለሐዋርያት ለሁሉ ሰለሆነ ሁሉም ደሞ ኢየሱስን የሚሰቅሉት ስላልሆኑ አታገኙኝም ማለቱ እንደማይሰቀል ነዉ የሚለዉን ሀሰብ ዉድቅ ያረገዋል እንደ ማያገኙት ለአይሁድ ተናግሯል ሚለዉ ሀሰት ነዉ ለአይሁድም ብቻ ሳይሆን ለመላዉ ሕዝብ ስለሆነ የተናገረዉ እንደማይዙት ለአይሁድ አንደመይሰቀል ተናግሯል ሚለዉ ሙግት በዚሁ ይፈረሳል ለምሳሌ እኔ የተጣለሁት ሰዉ አለብንል እኔ ለምሳሌዉ እንደ ከ
ክርስቶስ የተጠላሁት ልጅ እንደ አይሁድ ጓደኞቼ ቤተሰቦቼ ደሞ እንደ እስራኤል ሕዝብ ቢሆን እኔ የተጣላሁት ልጅ አለ እና አሱ ሊገለኝ ይፈልጋል እኔ ደሞ ሊገለኝ ለሚፈለገዉ ልጅ ልሄድ ነዉ ብዬ ሊገለኝ ስለሚፈልገዉ ልጅ አዉርቼ ከአሀገር ብወጣ ሊገለኝ የፈለገዉን ሰዉ ፈርቼ ነዉ ያስብላል ግን ሊገለኝ ለሚፈልገዉ ብቻ ሳይሆን የማይገሉኝን ያልተጣላሃቸዉ ቤተሰቦቼን ጓደኞቼን ጨምሬ ልሄድ ነዉ ካልኩኝ የምሄድበት ምክንያት ልጁን ስለፈራሁ እንዳይገለኝ ነዉ አያስብልም ምክንያቱም ለሁሉም ለማይገሉኝም ስለሆነ የተናገርኩት

ለምን አለ ለሚለዉ ጥያቄ ኢየሱስ ከሐዋርያትጋ አብሮ በመዋል በመብላት ከነሱጋ አብሯቸዉ አሳልፏል የመጣበትን አላማ መቤዠቱን ከፈፀመ በሀላ ግን እንደማያገኙት በፊት አብሯቸዉ እንደሚዉለዉ እንደ በፊቱ እንደማያገኙት የሚናገር አንጂ እንደማይሰቀል አደለም ዋና ሀሳቡ ለመሰቀል አንደመጣ ተናግሯልና ሲሰለሰም አትሰቅሉኝም አላለም እንደሚሰቀለ በግልፅ እንደተናገረዉ ሙስሊሞች እንደመሉት ከሆነ አልሰቀልም አትሰቅሉኝም ልትሰቅሉኝ ትፈልጋላችሁ ግን አታገኙኝም ብሎ እስለካልተናገረ ድረሰ ላለመሰቀል ነዉ ሚያስብልበተ ምክንያት የለም ስለዚህ ስለመሰቀሉ በ በግልፅ ስለተናገረ ሙስሊሞች አንደሚሉት አለመሰቀሉን ገልፆ ስላልሆነ አተገኙኝም ያለዉ ሙግታቸዉ በዚህም ይፈርሳል ምከንያቱም ስለ አለመሰቀሉ ጠቅሶ አደለመና አታገኙኝም ያለዉ

መፅሀፍ የሆነ ጥቅስ ብቻ ሳይሆን ሙሉዉን መረዳትና ማንበብ ያስፈልጋል ዩሀ7:33_34 ዩሀ8:21 ላይ ነዉ አንግዲ አታገኙኝም ያለዉ ግን መልሱ እዛዉ ላይ ኢየሱስ አታገኙኝም ያለዉ ከስቅለቱ ከትሳኤዉ በሀላ ያለዉን ነዉ ምክንያቱም እዛዉ ክፍል ላይ

“ኢየሱስ በመቅደስ ሲያስተምር በግምጃ ቤት አጠገብ ይህን ነገር ተናገረ ጊዜው ገና አልደረሰምና ማንም አልያዘውም።
ዮሐንስ 8፥20
“እናንተ ወደዚህ በዓል ውጡ እኔስ ጊዜዬ ገና ስላልተፈጸመ ወደዚህ በዓል ገና አልወጣም።
ዮሐንስ 7፥8
“ስለዚህ ሊይዙት ይፈልጉ ነበር፤ ነገር ግን ጊዜው ገና ስላልደረሰ ማንም እጁን አልጫነበትም።
ዮሐንስ 7፥30

ከላይ ባየናቸዉ ጥቅሶች መሰረት ጌታ አየሱስ አታገኝም ያለዉ ግዜዉ ሳይደረስ ነዉ እርሱ የተናገረዉ አታገኙኝም ያለበት ገና ከእነሱ ከመለየቱ በፊት ግዜዉ የሚደርስና ግዜዉን የሚጠባበቃት እንዳለ ያስረዳል እና ግዜዉና ሰአቱ በሚደረስበት ግዜ የሚከናወን እንዳለ ለመረዳት አያዳግትም ግዜዉ እንዳልደረሰ ካስረዳ በሀላ ነዉ እንደማያገኙት ሚናገረዉ
ግዜዉ ሳይደርስ ይለናል ያ ግዜ ምንድነዉ ስንል የሚሰቀልበት ነዉ ግዜዉ ሳይደርስ አታገኙኝም ብሎ መናገሩ ከተሰቀለ ግዜዉ ከደረሰ በሀላ ስላለዉ ነገር እየተናገረ መሆኑን እንረዳለን ምክንያቱም አታገኙኝም ከማለቱበፊት ግዜዉን ሚጠባበቃት አንዳለ ስለተናገረ ነዉ
አታገኙኝም ሚለዉ ንግግር ግዜዉ ከደረሰ በሀላ ስለሚፈፀመዉ ሀሳብ እንደሚያወራ ይናገረል

ከላይ ግዜዉ ሳይደረስ በፊት ገና ግዜዉ ደረሶ ከዛ በሀላ ሚፈፀመዉን ነዉ አታገኙኝም ያለዉ ምክንያቱም ተሰቅሎ ሞቶ ከእርገቱ በሀላ ከእርገቱ በፊት እንደነበረ በምድር ከእነሱጋ አይሆንምና

ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ።
— ሉቃስ 22፥14
ሰአቱ በደረሰ ግዜ ግዜዉ ሰላልደረሰ ሚለዉ ስቅለቱ ነዉ አንድንረዳዉ 👉ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ
— ሉቃስ 22፥14

የፋሲካ እለት ላይ ግዜዉ አንደ ደረሰ እናያለን ያ ግዜዉ ምድን ነዉ የክርስቶስ መከራ መያዙ ነዉ አዛዉ ክፍል ላይ 👉“እርሱም፦ ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤”
— ሉቃስ 22፥15

እንድገመዉ ሰአቱ በደረሰ ግዜ ምን ይፈፃማል መከራዉን አየን ቀጣይም ደሞ ስጋውን መቁረሱ ደሙን ማፍሰሱ ነዉ 👉ሉቃስ 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁹ እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና፦ ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።
²⁰ እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ፦ ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።

እንዲሁም የሰዉ ልጅ እንደሚሰቀል በነገራቸዉ ግዜ ማንም እንዳይናገሩ አዞአቸዋል ለምን ግዜዉ ገና ስለሆነ “እርሱ ግን፦ የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል በሽማግሌዎችም በካህናት አለቆችም በጻፎችም ሊጣል ሊገደልም በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ይገባዋል ብሎ ለማንም ይህን እንዳይናገሩ አስጠንቅቆ አዘዘ።”
— ሉቃስ 9፥21-22

ያቺ ግዜ እና ሰአት አልደረሰም የተባለው የክርስቶስ መከራ ሞት ደሙን ማፍሰሱ ነዉ
“እንዲሁም የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።”
— ማቴዎስ 20፥28
“እርሱ ግን፦ የሰው ልጅ ብዙ መከራ ሊቀበል በሽማግሌዎችም በካህናት አለቆችም በጻፎችም ሊጣል ሊገደልም በሦስተኛውም ቀን ሊነሣ ይገባዋል ብሎ ለማንም ይህን እንዳይናገሩ አስጠንቅቆ አዘዘ።”
— ሉቃስ 9፥21-22

እንደዚ ግዜዉ ሳይደረስ የሚለዉን ካየን አታገኙኝም የሚለዉ ገና ግዜዉ ከደረሰ በኃላ ከተያዘ ደሙን ካፈሰሰ መከራን ከተቀበለ በኃላ ስላለዉ ነዉ

እውነት ለሁሉ

15 Oct, 15:41


ግዜዉ እና ሰአቱ አንዳልደረሰ የተናገረበት አንቀጽ ያ ግዜ እና ሰአት ምን ሚደረገበት ነዉ ኢየሱስ የሚያዝበትና ተላልፎ ሚሰጥበት ግዜ ነዉ

“ሦስተኛም መጥቶ፦ እንግዲህስ ተኙ ዕረፉም፤ ይበቃል፤ ሰዓቲቱ ደረሰች፤ እነሆ፥ የሰው ልጅ በኃጢአተኞች እጅ አልፎ ይሰጣል።”
— ማርቆስ 14፥41

አታገኙኝም ብሎ ከመናገሩ በፊት ግዜዉና ሰአቱ እንዳልደረሰና ግዜዉና ሰአቱ ሲደረስ ሚፈፀም አንዳለ ያጠየቀበት ላይ ግዜዉና ሰአቱ በደረሰ ግዜ ተላልፎ ሚሰጥበት ግዜ ናት ከዛ በኃላ ነዉ ኢየሱስ አታገኙኝም ያለበት ምክነያት ግዜዉ በደረሰ ሰአተ ይዘዉት የመጣበትን ፈፅሞ ሞቶ ተነሰቶ እንደሚሄድና ከአርገቱ በኃላ ግን እንደበፊቱ እንደማያገኙት ሚናገረ ነዉ ከእነሱ ከመለየቱ አይሁዳዉያኑ ቢፈልጉት የማያገኙት ገና ሚጠብቃት ግዜን ከፈፀመ በኃላ ነዉ ቢፈልጉት ማያገኙት ያቺ ግዜ እና ሰአት ደሞ ኢየሱስ ሚያዝበት መከራ ሚቀበልበት ስጋዉን ሚቆርሰበት ደሙን ሚያፈስበት ግዜ ናት ግዜ እና ሰአት የተባለችዉ

ሌላኛዉ ኢየሱስ እንሚሄድ ከተናገረ በኃላ በዩሀ7:33_34 ላይ ወደ ታች ላይ ቁጥር 39 እንዲ ይላል: ኢየሱስ ገና ስላልከበረ መንፈስ ገና አልወረደም ነበርና።”
— ዮሐንስ 7፥39
መክበር ምንድነዉ መንፈሰ መዉረድስ

ኢየሱስ ስላልከበረ ማለቱ ለመሰቀል ተላልፎ መሰጠቱ እና መያዘ ነዉ ጌታ ለሐዋርያቱ ተላልፎ እደሚሰጠዉ ከሐዋርያት ዉስጥ አንድኛዉ ሲነግራቸዉ ማነዉ ባሉት ግዜ ቁራሽ ምሰጠዉ ነዉ ብሎ ነግሯቸዉ ነበረ ቀራሹን ከሰጠ በኃላ ይሁዳ ሰይጣን ገብቶበት አሳልፎ ሊሰጠዉ ሲሄድ የዛን ሰአት ጌታ የተናገራት አለ እሱም አሁን የሰዉ ልጅ ከበረ እናም መለስ ብለን ጌታ እንደመያገኙት ከተናገረ በኃላ ስላልከበረ መንፈስ አልወረደም ያለዉ አልከበረም ማለቱ ተላልፎ አልተሰጠም ማለት አንደሆነ ያስረዳናል እናም ኢየሱስ እንደማያገኙት ከነገራቸዉ በኃላ ገና ስላልከበረ ማለቱ ተላልፎሎ ስላልተሰጠ ስላልተያዘ ማለት ነዉ መከበር መጀመሪያ አለበት ያቺን መክበር ሰአቱ ከደረሰ በኃላ ነዉ አይሁድ እንዲሁም መላዉ ሕዝብ ማያገኙት ገና ሚጠብቃት ክብር አለች እሷ ሳትፈፀም ሁሉም ማንም ሊያየዉ አይችልም ምክንያቱም ምቀረዉ ሚጠብቃትን ክብር ከፈፀመ በኃላ ነዉና ለዛ ነዉ አታገኙኝም ያለዉ ከከበረ በኃላ ከተያዘ አላማዉን ከፈፀመ ከሞተ ከተነሳ በኃላ ሰላለዉ ነዉ አታገኙኝም ያለዉ

በዩሀ 13:31 ላይ ይሁዳ ኢየሱስን እንደሚያስይዘዉ ቁራሽ ከሰጠዉ በኃላ ቁራሹን ከተቀበለ በኃላይሁዳ ኢየሱስ የሰዉ ልጅ ከበረ ማለቱ ተላልፎ መሰጠቱን ስለደረሰ ነዉ ምክንየቱም ሙስሊሞች ሚያነሷት አታገኙኝም ሚለዉ ጥቅስ አታገኙኝም ካለ በኃላ (የሰዉ ልጅ እንዳልከበረ ይናገረልና የሀ7:39) ዩሀ13:31ላይ ከበረ ያለዉ ይህ መክበር የተባለዉ ኢየሱስ ከሐዋርያቱ አንድኛዉ አሳልፎ እንደሚሰጥ እና ይሁዳ ሰይጣን ገብቶበት ሊያስይዘዉ ሲሄድ ነዉ የሰዉ ልጅ ከበረ ያለዉ ከዛ ቀጥሎ
እናንተ ልትመጡ አትችሉም ባለ ግዜ
ጴጥሮስ እንደሚክደዉ ኢየሱስ ከነገረዉ በኃላ ጴጥሮስ እንደካደዉ ትዝ ሚለዉ ከተያዘ ተላልፎ ከተሰጠ በኃላ ነዉ ማር14:72

እና ስናጠቃልለዉ በዩሀ7:33_34 ላይ ኢየሱስ እንደ ሚይዙት የተናገረዉ ከስቅለቱ በኃላ ያለዉን ቁጥር 39 ላይ ክርስቶስ እንዳልከበረ ገና ይናገረል ከላይ የላቸዉ አታገኙኝም ያለዉ ለመፈፀም መጀመሪያ ገና የኢየሱስን መክበር የሚጠባበቅ ነዉ የኢየሱስ መክበር ምንድነዉ ስንል አንዱ ሰዉ አሳልፎ እንደሚሰጠዉ ተናግሯል ምልክቱኀንም ከተናገረ በኃላ ይሁዳ ሊያስይዘዉ ሲሄድ ነዉ የሰዉልጅ ከበረ ያለዉ ዩሀ13:26_31) ኢየሱስ መያዙ ተላልፎ መሠጠቱ ነዉ መክበር ሚል ቋንቋን የያዘ ሲሆን ዩሀ7:33_34 ) ላይ አንደማያገኙት የተናገረዉ መጀመሪያ የሰዉ ልጅ(አንዳልተያዘ እነዳልተሰጠ) እንዳልከበረ መናገሩ አታገኙኝም ለሚለዉ ገና የክርስቶስን መክበር የሚጠብቅ ሰላለ ከክብረቱ በኃላ ነዉ የኢየሱስ አለመገኘት ሚፈፀመዉ ሚጠብቃት ክብር ስላለ ከመለያየቱ በፊት
ከክብረቱ በፊት ገና አልከበረም ሚለዉ ከከበረ በኃላ ስላለዉ የሚያወራ አንጂ ከመክበሩ በፊት እንደማይያዝ አደለም ከልጅ ሚኪ

እውነት ለሁሉ

15 Oct, 12:21


brisbane
የአብርሃም ልጅ ነውና
ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል

@EOTCbook

ሉቃ19:9
ይህ ቃል መድኅነ አለም ክርስቶስ ስለ ዘኬዎስ የተናገረው ነው
።ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል አለ በቤቱ ስለ ነዋሪው ስለ ዘኬዎስ
የተነገረ ነው። ዘኬዎስ ለምን መዳን ሆነለት ? መልሱን በቅዱስ
ቃሉ ሲመልስልን እንዲህ ይላል
"የአብርሃም ልጅ ነውና"
"ነውና "የሚለው ግስ ለውጤቱ የቀረበ ምክንያት ለመሆኑ ቋንቋን
የሚያውቅ ሁሉ ይረዳዋል።
ወጤቱ ........መዳን
ምክንያቱ...የአብርሃም ልጅ
መሆን
ዘኬዎዝ የአብርሃም ልጅ መሆኑ ማረጋገጫው ምን ነበር ?
ጌታውን በቤቱ ከተቀበለ በኋላ ዘኬዎስ ድኛለሁ በቃኝ አላለም ስራ
ጀመረ ስራውም ይህ ነበር
"ጌታ ሆይ ካለኝ እኩሌታውን ለድሆች እሰጣለሁ ማንንም በሃሰት
ከስሼ ብሆን አራት እጥፍ እመልሳለሁ" ሉቃ 19:8-9
አዎን ለመዳን ክርስቶስን አምኖ መቀበል ብቻ በቂ ቢሆን የጌታ
መልስ እንዲህ ይሆን ነበር
"ዘኬዎስ ስለዳነ ስራ ሰራ"
ወይም ዘኬዎስ ጌታን በቤቱ እንደተቀበለ መዳኑ የተጠናቀቀ ቢሆን
ጌታ እንደገባ እንዲህ ባለ ነበር
" ዛሬ ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል"
ነገር ግን እንደገባም ይህን አላለም ጌታ ስለ ዘኬዎስ ቤት መዳን
የተናገረው ዘኬዎስ ካለኝ ለድሆች እሰጣለሁ ብሎ በጎ ሥራን
ሲሰራ ነው እንዲህ ያለው
"የአብርሃም ልጅ ነው ነውና ለዚህ ቤት መዳን ሆኖለታል"
የአብርሃም ልጅ ለመሆን የአብርሃምን ሥራ መሥራት ግድ ይላል
"የአብርሃምስ ልጆች ብትሆኑ የአብርሃምን ሥራ ባደረጋችሁ ነበር"
ዮሐ8:39
ዘኬዎስንም የአብርሃም ልጅ ያሰኘው እንደ አብርሃም በጎ ሥራን
መጀመሩ ነው አባታችን አብርሃም በሥራ ጽድቅን አምኖ
በመሥራት ጽድቅን መዳንን ተቅብሏል
" አባታችን አብርሃም ልጁን በመሠውያው ላይ ባቀረበ ጊዜ በሥራ
የጸደቀ አይደለምን ?"
ያቆ 2:21
ዘኬዎስም የአብርሃም ልጅ ነውና አንደ አባቱ እንደ አብርሃም አምኖ
ጌታውን በቤቱ ተቀበለ ከዛም ሥራን ጀመረ ያኔም እንዲህ ተባለ
"የአብርሃም ልጅ ነውና ለዚህ
ቤት መዳን ሆኖለታል"

ዲያቆን ሸዋፈራው አለነ

@EOTCbook
@EOTCbook

እውነት ለሁሉ

12 Oct, 16:21


https://youtu.be/F4BoxLk_cEg?si=5ynlz8JH-sE_qJeO

እውነት ለሁሉ

12 Oct, 13:59


ተመሳሳይ ኮፒ ፎርጅድ እምነት ሲኖርህ እንደዚ ነዉ ጰውሎስ እንዳለው
2ኛ ቆሮ 11
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ


¹⁵ እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤

እውነት ለሁሉ

12 Oct, 07:44


እኛም ደስ ብሎናል እግዚአብሔር ይመስገን 🥰🥰

“ለሚወጣ ሁሉ በክርስቶስም ትምህርት ለማይኖር ሰው አምላክ የለውም፤ በክርስቶስ ትምህርት ለሚኖር አብና ወልድ አሉት።”
2ኛ ዮሐንስ 1፥9

“ከዚህም በረት ያልሆኑ ሌሎች በጎች አሉኝ፤ እነርሱን ደግሞ ላመጣ ይገባኛል ድምፄንም ይሰማሉ፥ አንድም መንጋ ይሆናሉ እረኛውም አንድ።”
— ዮሐንስ 10፥16🥰🥰

እውነት ለሁሉ

11 Oct, 20:18


1ኛ ጴጥሮስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²⁰ ጥቂቶች ማለት ስምንት ነፍስ በውኃ የዳኑበት መርከብ ሲዘጋጅ፥ የእግዚአብሔር ትዕግሥት በኖኅ ዘመን በቈየ ጊዜ ቀድሞ አልታዘዙም።
²¹ ይህም ውኃ ደግሞ ማለት ጥምቀት ምሳሌው ሆኖ አሁን ያድነናል፥ የሰውነትን እድፍ ማስወገድ አይደለም፥ ለእግዚአብሔር የበጎ ሕሊና ልመና ነው እንጂ፥ ይህም በኢየሱስ ክርስቶስ ትንሣኤ ነው፤

እዉነታዉ እሄን ነዉ ሚሉን 😁

እውነት ለሁሉ

11 Oct, 07:40


መልአክ ከሰማይ ሲወርድ አየሁ፥ ከክብሩም የተነሣ ምድር በራች።”
  ራእይ 18፥1 አንዱ መልአክ ብቻምድርን ይሸፍናል ምድርን ሁሉ የሚሸፍን ባይሆን ምድር ሊያበራ አይችልም ለምሳሌ ጥላብንይዝ በያዝናት ቦታ ብቻ ጥላ ሀኖ ይሸፍናል እንጂ ሌላም ቦታ ጥላ አይሆን
ከቃሉም ስንነሳ መልክተኛ የሚል ትርጉም አለዉ አሄን መልእክተኝነት የሚታዘዙት የሚያዛቸዉ ጌታ እግዚአብሔር ብቻ ነዉ

ብዙ ግዜ ለነብያቶች ለሐዋርያት ከአምላክ ዘንድ እየተላኩ የእግዚአብሔርን ስራ ይፈፅማሉ ለምሳሌ ዘፀ 23:20
እና አየሱስ መልአክን መላክ ሚችል በስጋ የተገለጠ አምላክ ስለሆነ መልአክን እንደሚልክ ይነግረናል በምፅአት ግዜ.የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል፥ ከመንግሥቱም እንቅፋትን ሁሉ ዓመፃንም የሚያደርጉትን ይለቅማሉ፥”
  — ማቴዎስ 13፥41 ብዙ ጥቅሶች አሉ ፅሁፍ እንዳይበዛ ወደ ሀሳቡ ስንገባ ኢየሱስ መልአክን መላክ አንደሚችል እናያለን እና ኢየሱስ አይሁዳዉያኑን ያሰቀሉትና ያስገድሉት መልአኩን ልኮ መከላከል እና ጫፉን እንዳይነኩት ማረግ እየቻለ ለምን አላረገዉም?እንዲዉም ከላይ እነዳየነዉ በዩሀ ምዕ18 እንዳይዙት ማረግ ይችላል ሙስሊሞች አንደሚሉት በግዴታ የተፈፀበት ከሆነ መልአኩን ልኮ እንዳይነኩት ማረግ ይችላል እንዴት ግን መልአኩን ልኮ ሁሉን ነገር ማስቆም እየቻለ ለምን አላስቆመም ? ለምን ዝም አለ? መልሱ የኢየሱስ መሞቱ ሆነ በአይሁድ መንገላታቱ እርሱ ስለወደደ ና ስለፈቀደ እንጂ ሰዉ በመሆኑ ብቻ ተገዶ አደለም እርሱ ሰዉ ብቻ ሳይሆን ሰዉ የሆነ አምላክ ነዉና የኢየሱስን ስጋነት ብቻ በማንሳት ወደ ተሳሳተ አቅጣጫ ወደ ሞት እንዳትሄዱ ከልጅ ሚኪ የመዳን ቀን ዛሬ ነዉ በኢየሱስ አምናችሁ በመጠመቅ የዘለአለም ሕይወትን ተካፋይ ሁኑ የምትሰሙት ቃል ይፈርድባችሃልና ሉቃ 16:27-31

እውነት ለሁሉ

10 Oct, 18:49


"በአፉ መሳም ይሳመኝ ፍቅርህ ከወይን ጠጅ ይልቅ መልካም ነውና"መኃ1:1
ጌታዬ መድኃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ ኾይ ጠጥቸው በልቡናዬ ጊዜያዊ ደስታና ሐሴት ከሚሰጠኝ ምድራዊው የወይን ጠጅ ይልቅ ያንተ ፍቅር እጅግ መልካም ነው ።የፍቅርኽ ጥግ ወሰን የለውም። በምድራዊው ወይን አምሳል የሰጠኸኝ አማናዊው ቅዱስ ደምኽ ውስጤ ተዋሕዶ ዘወትር ስለፍቅር ቤዛ ያረከው አንተነትኽን እንድሻ ያደርገኛል። በሕብስቱ በኩል ቅዱስ ሥጋኽን ስመገብ ሰማያዊውን ምስጢር በመካፈል ምድራዊውን ግሳንግስ እንድረሳ አድርጎ ባንተነትኽ ውስጥ እንድሰወር ያደርገኛል።ጌታዬ ኢየሱስ ኾይ በአፍኽ መሳም ስመኸኝ በመሥዋዕትነትኽ ፍቅርኽን አሳይተኸኝ ዘወትር በብርሃንኽ ብርሃንን እያየኹኝ በቀራንዮ መስቀልኽ አብርሆት ኾኖልኝ ዘወትር ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንተን አመልካለው።ያበረታኸኝ ብርቱ የማትደክም አንተ እግዚአብሔር ነኽ ፤ ያጠነከርከኝ ጠንካራው የማይሰበር ጌታ ነው ፤ ከወደኩበት ያነሳኝ መውደቅ የሌለበት አምላክ ነው ፤ የተወልኝ የሚተው ንጉስ ነው ፤ የማረኝ መሐሪው ኢየሱስ ነው ፤ የቀባኝ የሚቀባ (ቀይጥበቅ)ክርስቶስ ነው ፤ ነውሬን የሸፈነው ነውር የሌለበት ንጹሑ በግ ነው ፤ ከፍ ያረገኝ በከፍታ ያለው ዳኛ ነው ፤ ኃጢአቴን ያስተሰረየው(ይቅር ያለው) ሊቀ ካህናቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ፤ ይቅር ያለኝ ታጋሽ ጌታ አማኑኤል ነው ፤ ያሻገረኝ ፋሲካችን ክርስቶስ ኢየሱስ ነው ፤ ያዳነኝ በምሕረቱ መድኃኔዓለም ነው። ወዳጆች ሆይ በአንድነት በሶስትነት የሚመለክ አምላካችን ሥላሴ ያላረገልን ነገር ያልሰራልን ሥራ የለም። ስንወድቅ አንስቶናል ፤ ወዳጅ ስናጣ ወዳጅ ሆኖናል ፤ ስንደክም አበርትቶናል
፤ ስንስት መልሶናል ፤ ስንሰበር ጠግኖናል ፤ በነፍስም በሥጋም ታመን ሳለ አድኖናል ፤ ፍርሃታችንን በድፍረት ፤ እስራታችንን በነጻነት
፤ መጠራጠራችንን በእምነት ፤ ዝቅታችንን በከፍታ ፤ ባዶነታችንን በሙላት......... ለውጦታል!! ክብር ምስጋና ውዳሴ አምልኮ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ይሁን አሜን!!
ዲያቆን ሸዋፈራው
https://t.me/orthodoxawitewahdo
ቻናሉን ተቀላቅለው ኦርቶዶክሳዊ ወንጌል ይማሩ!
ይቆየን

እውነት ለሁሉ

10 Oct, 10:58


The infallibility of the Church is the belief that the Holy Spirit preserves the Christian Church from errors that would contradict its essential doctrines. It is related to, but not the same as, indefectibility, that is, "she remains and will remain the Institution of Salvation, founded by Christ, until the end of the world."[1] The doctrine of infallibility is premised on the authority Jesus granted to the apostles to "bind and loose" (Matthew 18:18; John 20:23) and in particular the promises to Peter (Matthew 16:16–20; Luke 22:32)

እውነት ለሁሉ

09 Oct, 18:51


በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ተስፋ ቆርጠህ ጸሎትህን እንዳታቆም። ንስሓ እስከምገባ ድረስ ብለህ ጸሎት ካቆምክ መቼም ንስሓ አትገባም። ምክንያቱም ጸሎት ራሱ የእውነተኛ ንስሓ መግቢያ በር ነው።

ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ - የኤፍራጥስ ወንዝ ገጽ 87

እውነት ለሁሉ

08 Oct, 07:28


ከእስልምና ወደ ክርስትና 5ቤተሰብ
😍“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
— ዮሐንስ 14፥6