ወርቃማ ንግግሮች @golden_speech Channel on Telegram

ወርቃማ ንግግሮች

@golden_speech


ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና።

አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot

🍂

ወርቃማ ንግግሮች (Amharic)

እንዴት ነው ወርቃማ ንግግሮች እና የቴሌግራም እርስዎኛ ይዘቴ ስለነበር? ወርቃማ ንግግሮች ላይ አሉታዊ እንቅስቃሴዎችን እና ኮምፒዋችን እንዲሁም ሌሎች ታዳጊ አረፋላቸው። እናስከረካቸው ከሆነ በሳምንቱና መረጃቸው፣ እንቅስቃሴ ጋር አማካይ እንደሚያስተምሩበት እና በሳምንት የቴሌግራም ተጠቃሚዎችን ይሰራል። ወርቃማ ንግግሮችን ከአንደኛው አስተዋጽኦ እና እንድናደርግ በመባል ለራስን ላይ ይተዋላል። እሱንም ለ@Golden_SpeechBot ይዘቱ እናመሰከርናል። ከዚህ በፊት መረጃዎችን መካከል ለመከተል እና ለመቀየር የቴሌግራም የአዳግ ዜና ለእስከ መረጃ እንደዚህ ከተጣራ የእገዛ ቀን እንዳደረገ የአዳግ ዜና ለተቀናመረ እና መረጃዎች የቴሌግራምን ለእነሱ ለማክበር ይችላሉ።

ወርቃማ ንግግሮች

15 Feb, 08:57


☹️ኢህሳን 😤🔠🔠🔠🔠😤✈️


ይህ ቻናል ነፃ የስራ ማስታወቂያ የሚለቀቅበት ቻናል ነው☹️ ቻናሉ ለየት የሚያደርገው ሁሉም ነገር በነፃ መሆኑ ነው
☹️🙁🙁☹️🙁🙁🙁😭
ቻናሉን በበለጠ እንዲዳረስ join እንዲሁም ሼር በማድረግ የበኩላችሁን ተወጡ☹️

😣🙁🙁☹️🙁🥳🤩☹️
ቻናሉን ለመቀላቀል
🙁☹️⚡️

t.me/ihsan_jobs 🎁
t.me/ihsan_jobs 🎁

ወርቃማ ንግግሮች

14 Feb, 18:25


እውነት/ሀሰት

_በአላህና  በመልእክተኛው እንዲሁም በቁርአን መቀለድ ከእምነት ያስወጣል

⚙️ከትክክለኛው  መልስ ጀርባ የሚሰጣችሁ አድድ በማድረግ ተቀላቀሉ
    👇👇👇

ወርቃማ ንግግሮች

12 Feb, 19:20


"አላህ አዳዲስ ጅማሮዎችን ሲሰጥህ… የበፊት ስህተቶችን አትድገም።"
[ነጂብ መህፉዝ ]

ምናልባት ትናንትህ  በብዙ ስህተቶች ተሞልቷል። ትናንት ላይ ያባከንካቸው በርካታ እድሎች ይኖራሉ። ግን አስተውል ዛሬ አዲስ ጀንበር ወጥታለች… ጨለማውን የገረሰሰች ጀንበር… ስለዚህ አዲስ ጅማሮን አላህ ሲሰጥህ የትናንቱን ብኩንነትና ስህተት አትድገም።

ወርቃማ ንግግሮች

11 Feb, 22:18


~🍂

በጊዚያዊ ስሜቶች ለሚያስተናግዱህ ሰዎች ክፍት ሁን ብዬ አልመክርህም። ሲፈልጉህ እላፊ ተጠግተው የነፍስ ዓለም የሚያደርጉህና ስትፈልጋቸው ደግሞ ሽታቸው የሚርቅህ ዓይነት ሰዎች ማለቴ ነው። እና እዚህ ዓይነት ብቻህን የምትፋለምበት ግንኙነት ውስጥ ሰላምም ህይወትም የለም። መራራቅ የማያደበዝዘው፣ መከራና ደስታን የሚጋራና መከታ የሚሆን ግንኙነት ውስጥ ራስህን ኢንቨስት አድርግ። ጓደኞችህንም  በመመርጥ ላይ እያልኩህ ነው።

ወርቃማ ንግግሮች

11 Feb, 19:59


አዋጅ ሰዎች ሆይ ንቁ!!
ኢማናችሁን ጀድዱ። አካላችሁን በስፖርት መንፈሳችሁን በዒባዳ አንፁ። ማንነታችሁን በዚክር ገንቡ። መጪው ጊዜ ከባድ የዕልቂት ዓመት ነው። በኢማን ብርሃን ጨለማውን የሚሰነጥቁ ሰዎች ብቻ ነጃ የሚወጡበት ዘመን!! አላህ ለጦርነት የፈጠራቸው ሙጃሂዶች እንጂ የማይድኑበት ወቅት

አዋጅ ሰዎች ሆይ ንቁ!!
ምድርና ሰማያት የተመሰረቱባትን ቃል አጥብቃችሁ ያዙ። ፍጥረታት ወደዚህ ምድር የመጡባት፣ ይቅጣጩበት ዘንድ ቂብላ የተተከለባት፣ የጂሃድ ሰይፎች የተመዘዙባት፣ የአላህ መብት በባሪያው ላይ ሁሉ የተደነገገባት ቃል!! ላኢላሀ ኢለላህ!! በእርሷ መንገድ ኑሩ በእርሷ መንገድ እንደፀናችሁም ሙቱ። ራሳችሁን ለመጪው ጊዜ አዘጋጁ።

ወርቃማ ንግግሮች

09 Feb, 16:39


የአክሱም ሙስሊሞች ጭቆና በአክሱማዊቷ የቁርአን መምህርት (ኡስታዛ)

📍ሐምሌ 1984 አክሱም ላይ ምን ተፈጥሮ ነበር?

📍ይህ ፅሑፍ "አክሱማዊቷ የቁርአን መምህርት" በሚል ነሐሴ 1985 ከታተመው ቢላል መፅሔት የተወሰደ ነው።

"በትግራይ ክልል፤ አክሱም ከተማ ውስጥ የከፍተኛ 2 ቀበሌ 05 ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ሸምሲያ ሸህ ሷሊህ ለዲናችን መጠናከር የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በቅርብ የመከታተል እድል አጋጠመኝና አርአያነታቸውን ላወሳችሁ ወደድኩ።

ወ/ሮ ሸምሲያ ሸህ ሷሊሕ ከሰላሳ አምስት በላይ ህፃናትን ቁርአን በማስቀራት ታላቅ ተግባር የፈፀሙ የሙስሊሞች መኩሪያ ናቸው። እኚህ ደርባባ ወ/ሮ ሲናገሩ ረጋ ያሉና ገፅታው የበራ ነው። ቁርአን ማስቀራት የመጀመራቸው ጉዳይ ከአባታቸው ጋር የተያያዘ ነው። አባታቸው ሸህ ሷሊህ ቁርአን ያስቀሩ ነበር። እርሳቸው ሲሞቱ የቁርአን ትምህርቱ ተቋረጠ። በዚህን ጊዜ በአካባቢው የሚገኙ ሙስሊሞች ወ/ሮ ሸምሲያን "ለምን አንቺ አታቀሪም? እርሳቸው ሳሉም ብዙውን ጊዜ የምታቀሪና ቁርአኑን በሉህ (አነስተኛ ጣውላ) የምከትቢው አንቺው አልነበርሽምን?" ብለው ወተወቷቸው። ወ/ሮ ሸምሲያም "እናንተ ከተቀበላችሁኝ ደስታዬ ነው" በማለት ልጆቹን ሰብስበው ማቅራት ጀመሩ። ቁርአንን ለማስቀራት የሚከለክል ምክንያት /ዑዝር/ ሲገጥማቸው አንጋፋ ተማሪዎቸቸው በዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያሉትን እንዲያቀሩ ውክልና እንደሚሰጡ አውግተውኛል-በጣፋጭ አንደበት።

ወ/ሮ ሸምሲያ ቁርአን ማስቀራት ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ [1980ዎቹ] ድረስ አያሌ ተፈታታኝ ችግሮች ገጥሟቸዋል። ከእነዚህም ውስጥ ጎላ ብለው የተፈታተኗቸውን እንዲህ ሲሉ አወጉኝ። "እንደምታውቀው እኛ የአክሱም ሙስሊሞች የግላችን ቤት አልነበረንም። ሀብታምም ይሁን ድሃ የአክሱም ሙስሊም የሚኖረው በኪራይ ቤት ነበር። ቤት ለመስራት አይፈቀድልንምና! ይህ በኋይለስላሴ ጊዜ የነበረ ጭቆና ሲሆን ደርግ መጣና ሙስሊም አክሱም ውስጥ ቤት እንዳይሰራ የሚከለክለውን እገዳ አንስቶ መሬት ሰጠን። ታዲያ በክራይ ቤት እኖር በነበረበት ጊዜ ልጆችን ሰብስቤ ቁርአን ሳቀራ አከራዮቼ "ቤታችንን የልጆች መሰብሰቢያ አድርገሽ ልታፈርሺብን ነው..." በማለት በማቅራቴን እንዳቆም ይጠይቁኝ ነበር። እኔ ግን ጥያቄያቸውን አልቀበል ብዬ ማቅራቴን እቀጥላለሁ። እነርሱም ከቤታቸው ያስወጡኛል። እንደገና ሌላ ቤት ተከራይቼ ማቅራቴን እቀጥላለሁ። ትንሽ ቆይተው እነዚህም ይቃወሙኛል። እንዲህ እያልኩኝ የግሌን ቤት እስካገኝ ድረስ ከሀያ ቤቶች ተባርሬያለሁ።

ይህን ካወጉኝ በኋላ የትዝታ ቅኝታቸውን ወደቅርቡ ዘመን መለሱት። እናም እንዲህ አሉኝ። "እንደምታስታውሰው ሐምሌ 1984 በአክሱም ሙስሊሞች ላይ የ"ክተት" አይነት ዘመቻ ተጠንስሶ ነበር። በዚያን ጊዜ እኔ ከሌሎች ሙስሊም ጎረቤቶቼ በበለጠ ተሳድጃለሁኝ። የዚህም ምክንያት ቁርአን የማቀራ ስለሆንኩኝ ነው። አልሐምዱሊላሂ ጎረቤቶቼ ጋር ተደብቄም ቢሆን ነፍሴን አትርፌአለሁ። ሆኖም ግን እኛን ለማጥቃት የተነሱት ሰዎች እቤቴ ድረስ ገብተው የማቀራበትን ቁርአን ቀደድው ሉሑን ሰባብረው ቤቴ ላይ ያለ እቃ አንድ እንኳ ሳይቀር ሰባብረውብኛል።

በውይይታችን መሀል "እስላም የሴቶችን የመማር እድል ይነፍጋል" የሚለው የአላዋቂዎች አሉባልታ ድንገት ትውስ አለኝና ነገሩን አጠገቤ ካሉት እንስት መምህር ጋር አስተያይቼው በውስጤ ሳቅሁኝ። እናም "ሴት አስተማሪ /ቁርአን አቅሪ/ በመሆንዎ የደረሰብዎት ችግር አለን" ብዬ ለወ/ሮ ሸምሲያ ጠየቅኋቸው።

"በእውነቱ ሴት አቅሪ በመሆኔ አንድም የደረሰብኝ ችግር የለም፤ እንዲያውም ብዙዎች ይደሰቱብኛል። ባለቤቴም ለዲኔ በማደርገው እንቅስቃሴ ፍፁም ደስተኛ ከመሆናቸውም ባሻገር አጥብቀው ያበረታቱኛል። እንዳውም አንዳንድ ጊዜ ህመም ቢጤ ጫን ሲለኝና ድካም ሲበረታብኝ ህፃናቱ እንዳይጉላሉና እንዳልጨነቅ ብለው እርሳቸው ያስቀራሉ።" አሉኝ።

ወ/ሮ ሸምሲያ ቁርአን በማቅራት ላሳለፏቸው ረዥም አመታት በእጅጉ እንደሚያስደስታቸው አውግተውኛል። "አየህ" አሉኝ በጣፋጭ አንደበታቸው "ሌሊቱን ታምሜ አድሬ ጠዋት ተማሪዎቼ ሲመጡ በሽታዬ ይለቀኛል። መቼም እነሱን በማቅራቴ የሚሰማኝን ደስታ እኔን አንድ አላህ ብቻ ነን የምናውቀው። "

እኒህ የተባረኩ ወ/ሮ በአሁኑ ጊዜ [1985] ከሁለት መቶ ህፃናት በላይ በግቢያቸው ውስጥ ያቀራሉ። ልጆቹን ሰብስበው የሚያቀሩት በግቢያቸው ውስጥ በሚገኝ ጥላ ቦታ ላይ ነው። ይህ ቦታ ጠንከር ያለ ፀሐይ እንዳያጠቃቸው የሚከላከልላቸው ቢሆንም ቅሉ ዝናብ በሚዘንብበት ጊዜ ለማቅራት አመቺ አይደለም። ወ/ሮ ሸምሲያ እንደነገሩኝ ከሆነ አላህ በጭድ የተሸፈነ ጣሪያ ቢጤ ያለው ቤት እንኳ የመስራት አቅም ቢሰጣቸው በእጅጉ ይደሰቱ ነበር። ትልቁ ችግርና ጭንቀታቸውም ከፀሐይና ከዝናብ የሚከላከል ጎጆ ቢጤ መቀለሱና ህፃናቱም ተመቻችተው የሚቀመጡበት ወንበር አለማግኝታቸው ነው። ወ/ሮ ሸምሲያ ለዲናችን ከሚያበረክቱት ታላቅ አስተዋጽኦ አኳያ ያለባቸውን ችግር ከጎናቸው ሆኖ መቅረፉ የአህለል ኸይሮችን ትኩረት የሚሻ ይመስለኛል። የሚመለከተውም ክፍል ችላ ሊላቸው አይገባም ባይ ነኝ። "

_
በነገራችን ላይ ኡስታዛ አላህ ረጅም እድሜ ሰጥቷቸው አሁኑም በአክሱም ከተማ በህይወት አሉ። ከአንድ አመት በፊት Nur Quran Bank Islamic Association / ኑር የቁርኣን ባንክ ኢስላማዊ ማህበር ወደ አክሱም ተጉዘው በነበሩ ጊዜ በኔ ጥቆማ ቤታቸው ድረስ ሄደው እንደዘየሯቸው እና በነብዩ ሙሐመድ ሰላዋት ሲያወርዱ ቀርጿቻዋል።

ወርቃማ ንግግሮች

07 Feb, 19:05


~

ይህ የምድራችን ትልቁ ፍጥረት የሆነው ሰማያዊ ዓሳ ነባሪ ነው። ቁመቱ 30 ሜትር ይደርሳል። ክብደቱ 180ሺህ ኪሎግራም ይመዝናል። ይህም በአማካኝ 33 ዝሆኖች ያህል ማለት ነው። ልቡ ብቻ ቁመቱ 1.5 ሜትር ሲሆን ክብደቱ 180ኪሎግራም ነው። የሰው ልጅ የልቡን ያህል እንኳን ክብደት የለውም። እንዲሁም በአንዱ የልቡ የደም ቧንቧ ውስጥ ገብቶ በሌላኛው መውጣት ይችላል።

ይህ ግዙፍ የአላህ ፍጥረት ታዲያ ጌታውን ከመታዘዝ አይኮራም። ሰው ግን ከሁሉም በላይ ነኝ ብሎ ይንጠባረራል።

አላህም እንዲህ አለ፦

«በምድርም ላይ የተንበጣረረክ ሆነህ አትሂድ። አንተ ፈፅሞ ምድርን አትሰረጉድምና። በርዝመትም ፈፅሞ ጋራዎችን አትደርስምና።»
(ኢስራዕ 37)

ወርቃማ ንግግሮች

07 Feb, 14:11


🍃 ዱ ኒ ያ 🍂

ወርቃማ ንግግሮች

04 Feb, 18:33


👑          ⭐️             ⚡️
ٰ    • ○ ° 🌹🌹🌹• ○ °• ○ °• ○ °
 • ○    🌹🌹🌹🌹    • ○ °  👈አበባውን
• ○ °🌹🌹🌹🌹🌹           በመንካት• ○ °
  • 🌹🌹🌹🌹🌹🌹    ብቻ ምርጥ
○ 🌹🌹🌹🌹🌹🌹    የሱና 𝙘𝙝𝙖𝙣𝙣𝙚𝙡  ° :.
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹         ያገኛሉ📡
 • 🌹🌹🌹🌹🌹      ° :.   * • ○       
• ○  🌿🌹🌹🌿      
  • ○ °   🌿🌿            👈
     •        🌿   • ○ °        🌿🌿
 • ○ °        🌿     • ○ ° 🌿🌿🌿
   • ○ °         🌿       🌿🌿🌿🌿
    • ○ °          🌿  🌿🌿🌿🌿🌿
        • ○ °       🌿   🌿🌿🌿🌿
      • ○ °         🌿  🌿🌿🌿
          • ○ °     🌿  🌿° :. * • ○
         °• ○ °      🌿° :.   * • ○
                    🌿° . °☆  . * ● ¸
.    ★  🌿° :.   * • ○ °
        ° .     🌿. * ● ¸
                  🌿       በቀላሉ ይቀላቀላሉ ።
☆  . * ● ¸ .
★ ° . *   ° . °☆  . * ● ¸
.    ★  ° :.   * • ○
🅰️🅰️🅰️⭐️🔗🔡🔡🔡
ለተጨማሪ ሀሳብ አስተያየት  ጥቆማ
@twhidfirst1 ⭐️🔗🔡🔡🔡

ወርቃማ ንግግሮች

02 Feb, 07:19


➡️ኢህሳን jobs Advertising

ይህ ቻናል በሀገር ውስጥ ያሉ ስራ አጥ
            ወንድም እህቶች
በአላህ ፍቃድ  የስራ ማግኛ ሰበብይሆን ዘንድ
ታስቦ የተከፈተና የስራ ማስታወቂያ የምንለቅበት
አዲስ ⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️ ነው 

በቻናሉ ያለምንም ክፍያ የስራ ማስታወቂያ
የሚለቀቅበት ቻናል ሲሆን

እናንተም ወደቻናሉ በመቀላቀል የቻናሉ
አባል ሁኑ እናንተም ይህንንም ቻናል
ሼር በማድረግ የቻናሉን እድገት አስቀጥሉ

አላማችን ወንድምና እህቶቻችን ስራ አጥ
እንዳይሆኑ ሰበብ ማድረስ ነው
🔗ተቀላቀሉ

https://t.me/ihsan_jobs
https://t.me/ihsan_jobs

ወርቃማ ንግግሮች

31 Jan, 16:54


በሰው ተፈጥራዊ ቅርፅ ላይ አንድ ነገር ቢጨመርበት እንኳን አያምርም። እንዲሁ አንድ ነገር ቢቀነስ ያስጠላል።

የዓለም ሰዓሊዎችና ዲዛይነሮች ተሰባስበው በሰው ቅርፅ ላይ አንድ የሚያስውብ ነገር እንፍጠር ቢሉ አይችሉም። ወይም ይህ አያስፈልግም ብለው ቢቀንሱ ያስጠላልም፥ እንዲሁም ይበላሻልም።

ሌላው ቀርቶ ከሰው ተፈጥሮ ጋር የማይመሳሰል አዲስ ነገር እንኳን መሳል አይችሉም። ምሳሌ ስላልታወቁ ፍጥረታት (Aliens) የተሰሩ የአሜሪካ ፊልሞችን ካያችሁ ሁሉም ኤሊዬንሶች ከሰው ጋር የሚመሳሰሉና የሆነ ተፈጥሮ የጎደላቸው አስቀያሚ ፍጥረታት ናቸው። የዚህ ምክንያቱ በፊልሞቹ ላይ በርካታ “ጠበብት” ዲዛይነሮች ቢሰባሰቡም ከሰው የተለዬ አዲስ ፍጥረት መቅረፅ ስላልቻሉ ነው።

ይህ የሰው ልጅ በሌላ ሰው ወይም ፍጥረት ሊፈጠር ቀርቶ ሊሳል እንኳን እንደማይችል የሚያሳይም ነው።

አላህ የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ቅርፅ እንከን የሌለው የተሟላና የተዋበ እንደሆነ ሲነግረን እንዲህ አለ፦

❝ቀረፃችሁም! ቅርፃችሁንም አሳመረ።❞
(አት-ተጋቡን 3)

ወርቃማ ንግግሮች

30 Jan, 16:42


~

ለአመታት ግንባታው ተቋርጦ የነበረው የደሴው አንጋፋው የአረብገንዳ መስጂድ የሚናራ ግንባታ ስራ ተጀምሯል። የመስጂድ አስተዳደሩና የከተማው መጅሊስ ባደረገው ትግል የማስፋፊያ ቦታ በቅርቡ መሰጠቱ የሚታወስ ነው። በርቱ…

ወርቃማ ንግግሮች

30 Jan, 16:41


~ ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ


የጎሮው መስጅድ ኢማም መታሰራቸውን ሰምተናል። ምክንያቱም ደግሞ ለምን ዳእው ለምን አደረጋችሁ በማለት ጥዋት ላይ መታሰራቸውን ከቦታው የነበሩ አማኞች ተናግረዋል።

ዳእዋውን ያደረገውም ወንድም ወንድም ሬድዋን እኔ ነኝ ያደረኩት እሰሩኝ እኔንም በማለት እሱም አብሮ መታሰሩ ተሰምቶል። የታሰሩት ውጡ ቢባሉም ያ ሰረን አካል ለምን አሰረን በማለት ህዝቡም በቁጣ አንድ ላይ ይምጣና ያናግረን የከሰሰንም ካለ ይምጣ በማለት በፖሊስ ጣቢያ እንደታሰሩ ተሰምቶል

ወርቃማ ንግግሮች

30 Jan, 16:35


የነፃነቱ ጉድጓድ ባለ ድል!

ሴፕቴምበር 6/2021 ማለዳ ላይ እስራኤላዊያኑን ያስደነገጠ አንድ ክስተት ተከስቶ ነበር።ወራሪው "የብረት ቁልፍ" ብሎ ከሚጠራው እጅግ ጥብቅ ቁጥጥር ከሚደረግበት የጊልቦአ እስር ቤት ስድስት ታሳሪዎች ማምለጣቸው ተሰማ።በየት በኩል አመለጡ ተብሎ ሲፈለግ ወደ እስር ቤቱ የሚወስድ ረጅም ጉድጓድን ያገኛሉ።ታዲያ ታሳሪዎቹ ረጅም ቀናትን ከፈጀ ቁፋሮ በኃላ ከእስርቤቱ ማምለጥ ችለዋል።ይህ በወቅቱ የእስራኤል የደህንነት መረብን መበጠስ የቻለ ታላቅ ጀብዱ ሆኖ ተወርቶ ነበር።ታዲያ ይህን ታላቅ ሚሽን የመራውን የሹሀዳኡል-ቁድስ ብርጌድ አመራር የነበረው ዘከሪያ አዝ-ዙቤይዲና ሌሎችም ታሳሪዎች ከቀናት አሰሳ በኃላ በጠቋሚዎች ተባባሪነት ዳግም ይያዛሉ።
ዘከሪያ አዝ-ዙበይዲ ዳግም ሊፈረድበት በዳኛው ፊት ቆሞ የተናገረው ይህ ነበር:-
"አንዲት ክፍተት ካገኘሁ እጄን አጣጥፌ የምቀመጥበት ምክኒያት የለም።አሁንም ከእስር ወጥቼ ነፃነቴን ለማረጋገጥ እሞክራለሁ።"

ታዲያ ይህ ጀግና ከ3 ዓመታት የእስር ቆይታ በኃላ በፍልስጤማዊያኑ የትግል ቡድኖች ተፅዕኖ አንገቱን ቀና አድርጎ በበሩ በኩል ለመውጣት ችሏል።

ወርቃማ ንግግሮች

25 Jan, 15:17


የ #ዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ ለብሰው እንዳይገቡ በመከልከላቸው #በመስጂድ ውስጥ ለመቆየት መገደዳቸውን ተናገሩ!!!

#አርባ_አራት የሚሆኑ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ኒቃብ ለብሰው ወደ ግቢው እንዳይገቡ እንደተከለከሉና አንዳንዶቹም ከአምስት ቀናት በላይ በመስጂዱ ውስጥ ለመቆየት መገደዳቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ከአዲስ ስታንዳርድ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተማሪዎች፤ ቀደም ባሉት ዓመታት ኒቃብ መልበስ ይፈቀድ የነበረ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ “የደህንነት ስጋትን” በመጥቀስ ያለቅድመ ማስጠንቀቂያ ኒቃብ መልበስን እንደከለከለ ተናግረዋል።

በዲላ ዩኒቨርስቲ የሙስሊም ተማሪዎች ማህበር ሊቀመንበር የሆነው ኑረዲን አብደላ በበኩሉ ጉዳዩን ከዩኒቨርስቲው የስራ ሃላፊዎች ጋር በጽሑፍም ሆነ በአካል ለመፍታት የተደረጉ ተደጋጋሚ ጥረቶች መፍትሄ አለማምጣታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግሯል።

አክሎም “በርካታ ሙስሊም ተማሪዎች ላለፉት አምስት ቀናት በመስጂድ ውስጥ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ለፈተና መቅረብም ሆነ የሚጠበቅባቸውን አሳይመንት ለማጠናቀቅ አልቻሉም” ብሏል።

ወርቃማ ንግግሮች

25 Jan, 09:05


أشهد أنْ لا إله إلا الله وحده لا شريك له، وأشهد أن محمدًا عبده ورسوله

ወርቃማ ንግግሮች

23 Jan, 17:13


የዲላ ዩኒቨርሲቲ የኒቃብ ክልከላን በተመለከተ

    የደቡብ ኢትዮጵያ  እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በፃፈው ደብዳቤ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የኒቃብ ክልከላ ማድረጉንና ሴት ተማሪዎች ከትምህርት እና ከፈተና ፕሮግራም መስተጓጎላቸዉን በተመለከተ መፍትሄ እንዲሰጥበት ጠይቋል፡፡

የዩኒቨርሲቲዉ አመራሮች ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ጋር ባደረጉት ዉይይት ከደህንነት ስጋትና ሀይማኖትን ከማንጸባረቅ ጋር ተያይዞ ኒቃብ መከልከላቸዉን በቃል የገለጹላቸዉ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ኒቃብ የሚለብሱ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት እና ከፈተና ፕሮግራም ተስተጓጉለዉ እንደሚገኙ ጠቅሷል።

ጉዳዩን በተመለከተ የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሚመለከታቸዉ የመንግስት ተቋማት ጋር በመነጋገር መፍትሄ እንዲያበጅለት ስንል በአላህ ስም እንጠይቃለን በማለት ደብዳቤውን አጠናቋል።

ወርቃማ ንግግሮች

23 Jan, 12:42


🌺~•

https://t.me/Ibnu_Mohammed/s/78

ወርቃማ ንግግሮች

21 Jan, 20:26


የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር ሆኗል

📌 ምዝገባው ጥር 15 ይጀምራል።

የ1446ኛው የሀጅ እና ዑምራ ጉዞ ምዝገባ ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ የካቲት 21 ብቻ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል።

ምዝገባው ጥር 15/2017 በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር የምዝገባ ጣቢያዎች ይጀመራል።

የሳውዲ ሀጅ ሚኒስቴር ባስቀመጠው አሰራር መሰረት ያለው የምዝገባ ጊዜ አጭር በመሆኑ ሁጃጆች (ተጓዦች) በወቅቱ ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀርቧል።

የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።

ምክር ቤቱ " የጉዞው ዋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የታየው የዶላር ጭማሪና በአየር መንገዶች ላይ ያለው የትኬት ዋጋ መናር ዋጋው ከፍ እንዲል አድርጎታል " ብሏል። 

" የሀጅ ዋሃ ከዶላር አንፃር የ4,921 ዶላር ቅናሽ እንዲደረግበት ቢደረግም በብር ግን ጭማሪ አሳይቷል " ሲል ገልጿል።

ጠቅላይ ምክር-ቤቱ የአገልግሎት ዋጋን በመቀነስ በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በማጠፍና በሳውዲ የሚቀርበውን አገልግሎት ተመጣጣኝ እንዲሆን በማድረግ 108 ሺህ ብር ቅናሽ እንዲኖረው ማድረጉን አሳውቋል።

የዶላር ዋጋ ከፍ በማለቱ ግን ብሩ መጨመሩ ተገልጿል።

ባለፈው ዓመት ለአንድ ሀጅ ዋጋ አጠቃላይ ብር 329,000 እንደነበር ይታወሳል።


ዋጋው የሚቀመስ አልሆን ጎበዝ😡

ወርቃማ ንግግሮች

21 Jan, 05:43


መቀሌ


በዚህ ሰአት የሰሜን ኮከብ የምትባላዊ ከተማ መቀሌ በአክሱም እየተደረገ ባለው ግፍ አፈና ጭቆን አገፍግፎናል።

በሂጃባችን አንደራደርም ብለው ተሰባስበው ጎዳና ላይ ወጥተዋል።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Jan, 20:55


~~

ዲላ ዩኒቨርስቲ «ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ነው!» ብሎ ሙስሊም እህቶቻችንን እንዳይማሩ ከልክሏል።
እውነት ለመናገር፤ ኒቃብን እንደ ስጋት ከሚመለከቱ ጽንፈኞች በላይ የሃገር ስጋት የለም።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Jan, 13:47


~

ከአንድ ወጣት ጋር በፍቅር ትወድቃለች። በአንድ ጎጆ ውስጥ ለመኖር ወስነው ከቤተሰብ ጠፍታ ከጎንደር ከእሱ ጋር ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ። እስከዚህች ሰዓት ድረስ ሙስሊም መሆኑን አታውቅም ነበር። ቤተሰቦቹ እንደሚያካብዱና እንደማይቀበሏት ለዛም አክስቱ ጋር እንድታርፍ ሲነግራት ነበር ሙስሊም መሆኑን ያወቀችው!
ኋላ ላይ በየእምነታቸው ሊኖሩ ተስማምተው ጎጆ ተቀለሰ። ከሁለት አመታት በኋላ ግን በአንዲት እህት ( ጎረቤቷ) ሰበብ ከእስልምና ጋር ተዋወቀች! ለእስልምና ተረታችም! በተረታችበት ማግስት ግን ሕይወት መልኳ ሌላ ሆነ!

ክህደት! ህመም! ማጣት ! መገፋት........... የሕይወት መንገዷ ሆነ😥

ለእስልምና የተከፈለ መስዋትነት !......
በፅናት የመቆም ተምሳሌትነት... ብቻ ... ጌታዬ ስንት አይነት ባርያ እንዳለሁ ያየሁባት መንገደኛዬ ነች!

ወርቃማ ንግግሮች

20 Jan, 13:38


የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት በአክሱም ት/ቤቶች የሒጃብ ክልከላ በመቃወም ነገ በሚደረገው ሰልፍ ሁሉም እንዲገኝ ጥሪ አቅርቧል።

ሸኽ አደም አደም ዓብዱልቃድር ዛሬ በሰጡት መግለጫ መጅልሱ ሒጃብ ከተከለከለበት ከጥቅምት ጀምሮ ጉዳዩ በውይይት እንዲፋታ ለወራት ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ከታች የመጅልሱ መዋቅር ከወረዳው ጀምሮ ጉዳዩ በቀጥታ ወደ ሚመለከታቸው መ/ቤቶችና የስራ ኃላፊዎች በአካል በመቅረብና ለቁጥር የሚታክቱ ደብዳቤዎች በመፃፍ ሁሉም ብዙ ጥረት ማድረጋቸው አስተውቀዋል። ነገር ግን ድካሙ ውጤት ማምጣት አልቻለም። ስለዚህም ለነገ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርተናል። በሰልፉም ስለፍትህ የሚያሳስበው የእህቶቹና ልጆቹ መበደል የሚያስጨንቀው ሁሉም በሰልፉ ተገኝቶ ድምጹን እንዲያሰማ ጥሪ አቅርበዋል።

ሒጃቧ ትለብሳለች
ትምህርቷም ትማራለች‼️

ወርቃማ ንግግሮች

18 Jan, 00:48


╰ ዱንያ ላይ ያልጎደለው ማንም የለም፣
━━━━━━━━━━━━━━━
⎓ሰው ሆኖ ሀሳብ ያልተጫነው አልተፈጠረም፣
⎓ሕይወት ትንሽ ይሁን ትልቅ ከሁሉም ፍጡር የሆነ ነገር ቀንሳለች፣
⎓ሰው ሆኖ የሞላለት አንድም ሰው የለም።

⊖መጥፎ ሰው ማለት ሀሳብ በገባው ሰው ላይ ሌላ ሀሳብ የሚጨምር ነው።
ጭንቀት በወረሰው ላይ ተጨማሪ ጭንቀት የሚለቅ ነው።
⊖ለሰው ችግር መፍትሄ መሆን ባትችሉ እንኳ ችግሩን ከአንድ ወደ ሁለት አታሳድጉ።╯

ወርቃማ ንግግሮች

17 Jan, 12:42


https://t.me/+YNVhq_7DnrVmOGQ0

ወርቃማ ንግግሮች

17 Jan, 12:41


ባልና ሚስት ይጣሉና ሽማግሌ ይሰበሰባል። ከዚያም ሁለቱም ችግራችሁን ተናገሩ ሲባሉ ...
ባል፦ "እኔ ከስራ ደክሞኝ ስመለስ ማረፍ እፈልጋለሁ። ነገር ግን ልጆችን እያንጫጫች አያሳርፉኝም" አለ
ሽማግሌዎቹም "ሌላስ?" ይሉታል
"እኔ ከስራ ስመለስ ልጅ ያዝ ትለኝና ወጥ ትሰራለች። የልጅ ወተት ታፈላለች። ምናለ ሳልመጣ ጨርሳ ብጠብቀኝ ተቀምጣ እየዋለች" ይላል በንዴት።

ሚስትም በሰዎቹ ፊት "ከዚህ በኃላ በፍፁም አንረብሸውም" ብላ ይቅርታ ስለጠየቀች ሽማግሌዎቹ ትተዋቸው ይሄዳሉ።

በነጋታውም ሚስት ልጆቿን ይዛ እናቷ ቤት ሄደች። ከስራ ሲመጣ ቤቱ ተቆልፏል። ልክ ከፍቶ ሲገባ ቤቱ እጅግ ይቀዘቅዛል። ከሰል ለማቀጣጠል ቢሞክር እምቢ አለው። ልብሱን ደራርቦ ሚስት ሰርታ የነበረውን
ጠራርጎ በላ። ዝምታው ሲጨንቀው ቴሌቪዥን ከፍቶ ለማየት ሞከረ ግን የለመደው የልጆቹ ድምፅ ናፈቀው እና እየከፋው ተኛ።

ጠዋት ሲነሳ ያ የሚጣፍጠው ቁርስና የሚወደው የሚስቱ ፈገግታ የለም። ከፋው። ፊቱን ታጥቦ ወደ ስራው ሄደ። ቁርሱንም ውጪ በላ ግን አላረካውም። ቀኑ እንደከበደው ዋለ። ስልኩን ቢያይም አትደውልለትም። ውሎ ሲመለስ ራቱን ውጭ በልቶ ከጓደኞቹ ጋር ቢያመሽም በመጨረሻ ያ ባዶ ቤት ጠበቀው። ለቅሶ ቤት ይመስል መግባት አስጠላው። ዞር ብሎ ሲያስብ ለካ ያለ ሚስቱ ጎዶሎ ነው።
ለካ ልጆቹ ረባሾቹ ሳይሆኑ አጫዋቾቹና የመንፈስ እርካታው ናቸው።

ከዚያ በኃላ "በእጅ የያዙት ወርቅ ሆናችሁብኝ ጥቅማችሁን ስላልተረዳሁ በጣም በድያችኃለሁ። እባክሽ ይቅር በይኝ ውዷ ሚስቴ!" ብሎ በሽማግሌ ታረቃትና በሰላም ኖሩ።
***
መልዕክቱ፦ ሚስቶች ሸክሞች ሳይሆኑ የቤቱ ተሸካሚዎች፣ ሰራተኞች እና አስተዳዳሪዎች ናቸው። ልጆች የቤቱ ሁከት ፈጣሪዎች ሳይሆኑ ደስታና ሙቀት ፈጣሪዎች ናቸው።
ስለዚህ ደስታ የሚሰጠንን ነገር ከማጣታችን በፊት ቀድመን ለይተን አውቀነው ተገቢውን ቦታ እንስጠው ለማለት ነው።

ወርቃማ ንግግሮች

14 Jan, 09:02


ሙስሊሟ ተማሪ በአክሱም ትምህርት ቤቶች ሂጃብ ለብሳ እንዳትማር የከለከለው በዋነኛነት የትግራይ ክልል መንግስት  ሲቀጥል የፌዴራሉ አካል ሙሉ ፍላጎት ስለሆነ ብቻና ብቻ ነው። ተጠያቂዎቹም የችግሩም ባለቤቶችም የትግራይና የፌዴራል መንግሥታት ብቻና ብቻ  ናቸው።

ለምን እውነቱን ሸፍኖ ሌላን መውቀስና ማስመሰል አስፈለገ?  ቢፈለግ  እኮ የክልሉ መንግስት በአንድ ቀን በአንድ  መንግስታዊ ትዕዛዝ ብቻ አይደለም ሂጃብን መስጂድ እና የመቀበሪያ ቦታን እንኳን የአክሱም ሙስሊሞች እንዲያገኝ ማድረግ ይችላል።

ታዲያ እውነቱ በዋነኝነት የትግራይ ክልል መንግስት እንዲሁም ሲቀጥል የፌዴራሉ አካል ፍላጎት መሆኑ በግልፅ እየታወቀ  ለምን በጥቂት የአክሱም የሰፈር ፅንፈኞችና ዱርዬዎች ላይ ጥያቄ  ማንሳት አስፈለገን? ለምንስ ዛሬስ እዚያው የማስመሰል ጥያቄዎች ላይ ቆምን?  ለዚያ ነው ማለት ነው ከፌዴራል እስከ ክልሎች ሁሉም መጅሊስ በሚባል ደረጃ መግለጫ ያወጣበትን ሁሉም ሙስሊም የጮኸበትን አንድ ችግር የማይሆን  ተራ ጉዳይን ሰምቶ መልስ የሚሰጥ መንግስታዊ አካል የጠፋው?  መልሳቹ በፍጹም አይደለም የሚል እንደሚሆን ግልፅ ነው ። ታዲያ ከዚህ በላይ መንግስታቶች በሙሉ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ያላቸውን ንቀት እና ሙስሊሙ አሁን ያለበት ተጨባጭ እውነት ለማየት ምን ማስረጃ ይቅረብ?  ስለዚህ የማስመሰል ጥያቄዎችን አቁመን ችግሩን ከስር መሰረቱ ለመንቀል የችግሩን ምክንያት ትቶ ሌላ ቦታ መኳተናችንን ካልቆምን ቀጣዩ ጊዜ እጅግ የከፋ ነው።

ወርቃማ ንግግሮች

12 Jan, 18:17


📣  የመጀመሪያው ፕርግራምተጀመረ 🔈
​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•


📚 ኡስታዝ አቡ ዚክራ ⭐️
      ተ
⭐️
             ጀ
⭐️
                  መ
⭐️
                          ረ
⭐️
ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም!

ሊንኩን ለሌሎችም ሼር አድርጉት

 ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘ ➘ ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘
t.me/tdarna_islam?livestream
t.me/tdarna_islam?livestream

ወርቃማ ንግግሮች

12 Jan, 15:56


🤲🤲
📣📣📣😋🥳😄🫣😬
💙ልዩ የዳዕዋህ ፕሮግራም
በትዳርና ኢስላም ቻናል


🎁ዛሬ እሁድ 🎁

የዕለቱ ተጋባዥ ⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️
💙🔤🔤🔠🔤🔤🔤🔤🔤🅰️🔤

💙🅰️🅰️🅰️ 🅰️🅰️🅰️🅰️🅰️


😄ርዕስ በሰአቱ ይነገራል

💙ዛሬ/እሁድ ከምሽቱ 3:00

🔠🔠🔠🔠
🔗@tdarna_islam👈
🔗@tdarna_islam👈
🤲 🤲 🤲

ወርቃማ ንግግሮች

10 Jan, 02:06


ይህ የሆነው መካ እንደተከፈተች ነው።አብደላህ ኢብን ሰዕድ ኢብን አቢ-ሰርህ ከሰለመ ቡኃላ ቁርዓንን የመመዝገብ ክብር የተሰጠው ሶሃባ የነበረ ሲሆን ለዲኑ ሲል ወደ መዲና ተሰድዶ እያለ በሆነ አጋጣሚ ወደ መካ ይመለስና እዚያው ሲቆይ ከኢስላም ተቀልብሶ ወጥቶ ወደ ቀደመ ጣዖታዊ ኣምልኮቱ ተመልሶ መካ እስክትከፈት ድረስ ኖረ።ነብዩ (ሰ.ዓ.ወ) ድል አድርገው መካን ከፍተው አጠቃላይ ምህረት ሲያደርጉ ጥቂት ሰዎች ይህን እድል ኣገኙም ነበር።ከእነዚያ ሰዎች መካከል አብደላህ ኢብን ሰዕድ ኢብን አቢ-ሰርህ አንዱ ሲሆን መስሊሞች በካዕባ መጋረጃ ላይ ተንጠልጥሎ ቢያገኙትኳ እንዲሰይፉት/እንዲገድሉት ነብዩ (ሰ.ዓ.ወ) ትዕዛዝ አስተላልፈውበት ነበር።

አብደላህ'ም ይህ እንደሚገጥመው ተገንዝቦ ስለነበር በቀጥታ ወደ ኡስማን ኢብን አፋን (ረ.ዓ) በማምራት ከዚህ ጉድ እንዲያወጡት ተማጸናቸው።።አብደላህ እና ኡስማን ኢብን አፋን (ረ.ዓ) የጥቢ ወንድማማቾች ነበሩ።

ኡስማን (ረ.ዓ) አብደላህን ወደ አላህ ነብይ (ሰ.ዓ.ወ) ይዘውት በመምጣት ለደህንነቱ ዋስትና ጠየቁለት።የአላህ ነብይ (ሰ.ዓ.ወ) ግን ለረዢም ሰዓት ዝም ብለው ከቆዩ ቡኃላ በመጨረሻ "ይሁን" አሉ።ይቅርታውን ተቀብለው ዐብደላህ እና ኡስማን (ረ.ዓ) ወጥተው ከሄዱ ቡኃላ የአላህ ነብይ (ሰ.ዓ.ወ) በዙሪያቸው ያሉትን ባልደረቦቻቸውን "ከመካከላችሁ ለረዢም ጊዜ ዝምም ማለቴን ያየ ጮሌ ሰው ተነስቶ አይሰይፈውም/አይገድለውም ነበርን?" አሉ።ባልደረቦቻቸውም በዚህ ጊዜ "የአላህ ነብይ ሆይ! በአይኖችዎ የሆነ ምልክት አያሳዩንም ነበርን?" ሲሏቸው።ነብዩ'ም (ሰ.ዓ.ወ) እንዲህ አሉ ፦ "ነብይ በአይን ጥቅሻ ሰውን አይገድልም።" በሌላ ዘገባ ደግሞ "ለአንድ ነብይ ከዳተኛ አይኖች ሊኖሩት አይገባውም" ማለታቸው ተጠቅሷል።

እዚህ ላይ "ከዳተኛ አይኖች" የተባለው አገላለጽ አንድ ሰው በአንደበቱ የሚናገረው እና በአይኖቹ የሚያሳየው ምልክት ለየቅል ሲሆኑ ነው።ለምሳሌ አንድ ሰው ከአንደበቱ አዎንታዊ ቃላትን እያወጣ በአይኖቹ ግን ከአንደበቱ የማይገጥም ምልክት ሊያሳይ ይችላል።እናም ነብያት እንዲህ እንዲያደርጉ አይፈቀድላቸውም ማለት ነው።

ኢብን ሒሻም (አላህ ይዘንላቸውና) እንደፃፉት "አብደላህ ኢብን-ሰርህ (ረ.ዓ) ከዚያ ቡሃላ ጥሩ ሙስሊም መሆን ችሏል።ዑመር (ረ.ዓ) በኸሊፋነት ዘመናቸው በተለያዩ የሃላፊነት ቦታዎች ላይ ያስቀመጡት ሲሆን ኡስማን'ም (ረ.ዓ) በተመሳሳይ መንግስታቸውን እንዲያገለግል ዕድል ሰጥተውታል።" ብለዋል።ኢብን ከሲር (አላህ ይዘንላቸውና) ደግሞ " አብደላህ ኢብር ሰርህ በቤቱ የፈጅር ሰላትን እየሰገደ (ሱጁድ ላይ ሆኖ) ወይም ሶላቱን አጠናቆ ነው የሞተው" ብለዋል።

ለአለማት ዕዝነት - 794-795

ወርቃማ ንግግሮች

10 Jan, 01:25


ምድር ገፅታዋን ልትቀይር ተሰናድታለች። ኺላፋውን ለሙስሊሞች ልታስረክብ ተዘጋጅታለች። የሙስሊሞች የከፍታ ዘመን ጅማሮ የኩ#ፍ#ር ኃይላት የሚፍረከረኩባቸው አመታት እነሆ አንድ ብለዋል። በየሀገሩ ምድር መልዕቷን እየሰደደች በምልክቷ እያወራችን ንቁ ትለናለች።

በዚህች ምድር ላይ ሙስሊሞች ዳግም የበላይ ይሆናሉ ኢንሻ አላህ። ቁድስ ነፃ ትወጣለች። ፍትህ ይሰፍናል። ግና ለአጭር ጊዜ ብቻ!!! ከዚያማ ሰማይ ምድሩ የሚናጥበት ፈተና ይቀጥላል። ደጃልና ኢሳ የዕጁጅና መዕጁጅም ይከታተላሉ። ምድር ትሰነጣጠቃለች። ትርገፈገፋለች።

እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ ንቁ

የሆሊውድ ምድር የአሜሪካዋ ሎስአንጀለስ በከባድ የሰደድ እሳት እየነደደች ትገኛለች።  በአራት አቅጣጫ የተነሱትን እነዚህን አውዳሚ  እሳቶች ለመቆጣጥ ከአቅም በላይ ሆኗል። ነዋሪዎቿ ተፈናቅለዋል። ኃብት ንብረታቸውን ትተው ተሰደዋል።


=          Mahi Mahisho

ወርቃማ ንግግሮች

08 Jan, 05:25


😋
📣የዳዕዋህ ፕሮግራም

😓የፕሮግራሙ አቅራቢ፦
1️⃣ኡስታዝ ዐብዱረዛቅ አልባጂ
ርዕስ፦ስለ ተቅዋህ
2️⃣ኡስታዝ አቡ ሒበቲላህ
ርዕስ፦ስለ ሞት
3️⃣ኡስታዝ ኑረዲን አል ዐረቢይ
ርዕስ፦ስለ ሶብር


✈️መድረክ መሪ፦ወንድም አቡ ሑዘይፋህ

0️⃣0️⃣0️⃣የሚተላለፍበት ቻናል፦
📥📥📥📥📥📥
t.me/tdarna_islam

😮ዛሬ እሮብ ከምሽቱ 3:30😓

ወርቃማ ንግግሮች

08 Jan, 00:26


አረብ ሀገር ላሉ እህቶች ቤተሰብና አፈ ቀላጤ ወንዶች ብራቸውን እየጨረሱባቸው ስለሆነ በተመጣጣኝ ዋጋ የማህበር ቤት እንሰራለን የሚሉ አጭቤዎች መጥተዋል ተጠንቀቁ

ወርቃማ ንግግሮች

07 Jan, 21:40


እነዚህ ወፎች ጎጃቸው ውስጥ ደርቀው ሞተዋል
ምክንያቱ ደግሞ ምግብ ለማምጣት የወጣችው እናታቸው በአንድ ወንጭፈኛ ተገድላ ነው እነርሱም አቅም ኖሯቸው አይበሩም እሷም ከአንድ ጨካኝ እጅ ላይ ወደቀች.................
ለሌሎች መሞት ምክንያት አትሁን አንድን ሰው ስታጠቃ እና ህልሙን ስታጨናግፍ ከጀርባው የብዙዎችን ህይወት አብረህ እያጨለምክ ነው።

ለማንም ህልም መሞት ምክንያት አትሁን
ቢቻልህ ተስፋ ስጥ። 👌👌👌

ወርቃማ ንግግሮች

07 Jan, 20:02


ሚስት ባሏን ልትፈትን ፈለገች ፣ ከኔ ተለይቶ ሲያድር ወይም ድንገት ከቤት ሲያጣኝ ምን ይሰማዋል? የሚለውን ለማወቅ አቀደችና ባለቤቷ ከሥራ በሚመለስበት ሰአት ጠብቃ አልጋ ስር ተሸሸገች።

~ በብጣሽ ወረቀት " ቤተሰቦቼ ጋ ሄጃለሁ። አልመጣም አትጠብቀኝ" የሚል ማስታወሻ ፅፋ ኮሞዲኖ ላይ አስቀምጣ አልጋ ስር ገባች።

~ ባል ወደቤት ሲገባ ባለቤቱ የለችም። ወረቀቱን አነበበና እሱም
መልስ ጫር ጫር አድርጎ ወረቀቱን ያገኘበት ቦታ አስቀመጠውና ልብሱን መቀያየር ጀመረ። ልብሱን ቀይሮ እንደጨረሰ ሞባይሉን አነሳና " ሄሎ ፍቅሬ የኔ ማር እንዴት ነሽልኝ ፣ ዛሬ ምርጥ ጊዜ እናሳልፋለን። ባለቤቴ ቤተሰቦቿ ጋ ሄዳለች አትመጣም። …… አንቺ ኮ ማር ነሽ…… እሷን ሳላገባ ባውቅሽ ኖሮ እሷን አላገባም ነበረ … … ከአምስት ደቂቃ በላይ አልቆይም ዝግጁ ሁነሽ ጠብቂኝ መጥቼ ወስድሻለሁ …… ባይ የኔ ጣፋጭ " ብሎ ወሬውን ጨርሶ ተነስቶ ወጣ።

~ ሚስት አልጋ ስር ሆና ቅጥል ብግንግን ብላለች… … ልክ እንደወጣ አፍናው የቆየችውን ለቅሶዋን አፈነዳችው…… ከዚያ ምናባቱ ነው ፅፎ ያስቀመጠው… … አለችና ወረቀቱን አንስታ ስታነበው……
" ቂሎ ባንቺ ቤት መደበቅሽ ነው አይደል…… እግሮችሽን ገና ስገባ ነው ያየሁት…… በይ እራት ገዝቼ መጣሁ እንባሽን ታጥበሽ… … እሽቅርቅር ብለሽ ጠብቂኝ " ነበረ የሚለው።         ፍቅር

ወርቃማ ንግግሮች

04 Jan, 03:45


ከእንቅልፌ የሆነ ነገር ቀሠቀሠኝ :: የመሬት መንቀጥቀጥ መሆኑን አላወቅኩም ነበር።

መሬት ፍጡር ናት ! ትዕግስቷ አላቂ ነው:: ስናበዛው መሰልቸቿ አይቀሬ ነው፡፡ ትክክት ሲላት ..ኧረ ወዲያ .. ብላ አሸቀንጥራ ከላይዋ ላይ ለማራገፍ እየሞከረች ነው። ሚስትህ ብትወሰልትብህ ፣ ጥጋብ ቢጫወተባት ፣ ሁለ ነገሯ ለመኗኗር የማይሆን ሆኖ ብልሽትሽት ብትልብህ ፣ ምን ብትወዳት ፣ የቱንም ያክል ሰፊ ብትሆን እንኳ ከትዳርህ ታርግፋታለህ ! መሬትም ይህንኑ ነው ለማድረግ እየሞከረች ያለችው ::

የሚታየው ፣ የሚሰማው ፣ የሚነገር የሚሰበከው ፣ የሚደነቅ የሚወደሠው ሁሉ ልሽቀትነት ፣ እኩይነት ፣ ብልግና፣ ወራዳነት ፣ ግፍ እና ነውረኝነት ፣ ጋጠወጥነት እና በዳይነት ሲሆን ...

ብልግና ሲወደስ ፣ ግፍ ሲሽሞነምን ፣ አረመኔነት ሲወገን ፣ ነውር ጌጥ ሲሆን ፣ ወራዳነት ሲያስከብር ፣ ጃሂል በሕዝብ ልብ ላይ ሲነግስ ፣ ሽማግሌ ሲረክስ ....

ግድያ ፣ ጭፍጨፋ በሚንበር እና በቤተ መቅደስ ሳይቀር ፅድቅ ሲሆን፣ ዙልም ኢባዳ መስሎ ሲታይ ፣ በአጥንት ቆጠራ የበሰበሰ ህሌና ተሸካሚው ሲበዛ ---

መሬት ይ ስለቻታል። መሬት ትክክት ይላታል። በቃ ደብረናታል 🤔 ወዲያ ከላየ ላይ አራግፍልኝ እያለች ነው!

ደጋግማ ተንገሸገሸች እኮ ! ዝግንን አደረጋትኮ !

ወርቃማ ንግግሮች

03 Jan, 22:11


በየትኛውም ሁኔታ ሂጃብ ሊከለከል አይገባም"

▣ የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ለሀሩን ሚዲያ ከገለጹት

- ሀሩን ሚድያ፣ ታህሳስ 25/2017

የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በትግራይ ክልላዊ መንግሥት በአክሱም ከተማ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሒጃብ ምክንያት እየደረሰባቸው ያለውን የመብት ጥሰት ለምን አላወገዘም ብሎ ሀሩን ሚዲያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለን ጠይቋል።

ዋና ፀሀፊው በምላሻቸው ከኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥያቄ አልቀረበልንም ነበር ያሉ ሲሆን በትላንትናው ዕለት ግን የመጅሊሱ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ በትግራይ በአክሱም ከተማ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን በደል እንድናወግዝ መጠየቃቸውን ገልፀዋል።

በቀጣይ ሰባቱም የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ አባቶች ውይይት አድርገን የደረስንበትን የምናሳውቅ ይሆናል ሲሉ ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል።

አክለውም የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በትግራይ ክልል ቅርንጫፍ የሌለው በመሆኑ ጉዳዩን ለማጣራት እንደተቸገረ ገልፀው የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዛሬ ያወጣውን መግለጫ አልተመለከትኩትም ብለዋል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ እንደ ግል አመለካከቴ በየትኛውም ሁኔታ ሂጃብ ሊከለከል አይገባም ያሉ ሲሆን ይህን የሚያደርጉ አካላት አስነዋሪ ተግባር መፈጸማቸውን አክለው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ የሰጡትን ምላሽ ከቆይታ በኋላ ወደናንተ ምናደርስ ይሆናል።

© ሀሩን ሚድያ

ወርቃማ ንግግሮች

03 Jan, 18:03


🌀  ታላቁ ፕርግራማችን ተጀመረ 🔈
​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•


📚 ሀላችሁም ተጋብዛቹኋላ ⭐️
      ተ
⭐️
             ጀ
⭐️
                  መ
⭐️
                          ረ
⭐️
ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም!
ሊንኩን ለሌሎችም ሼር አድርጉት

 ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘ ➘ ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘
t.me/merkez_abu_fewzan?livestream
t.me/merkez_abu_fewzan?livestream

ወርቃማ ንግግሮች

02 Jan, 21:29


ይሄን መፅሃፍ ዱባይ ወይም ኢማራት ላይ ያላችሁ የምትፈልጉ እንብበው።

የምትፈልጉ በኮሜንት መስጫው አውሩኝ።

ወርቃማ ንግግሮች

02 Jan, 21:28


“ይሔን ሰው ስትመረምሩ ተጠንቀቁ! እንዳይፅፍባችሁ" አለ የምርመራውን ቢሮ አንኳኩቶ ከፍቶ የገባው የደህንነት ሰው፡፡ ሥፍራው ማዕካላዊ ነበር፡፡ ኮማንደር ተኽላይ መብራህቱ ቢሮ። ኮማንደር ተኽላይ መብራህቱ ማን እንደነበር ምን አሳወቃችሁ?! እሱ የፀረ ሽብር ዲቪዥን ዋና አዛዣ አልነበረምን? እናም አንኳኩቶ የገባው የደህንነት ሰው በቁሙ በለቀቀው ወሬ የመርማሪዎቹ ትኩረት በአንዴ ወደሱ ተሳበ፡፡ እርሱም ወንበር ስቦ ተደላድሎ ተቀመጠ፡፡

ስለኔ የሚያውቃትን ሁሉ አንድ በአንድ ተረተረላቸው፡፡ ቀለማቸውን ቃል መያዣ ወረቀታቸው ላይ አጋድመው ሰሙት፡፡ ወደኔም ገልመጥ እያሉ በግርምት አስጨረሱት፡፡ በግምት ከግማሽ ሰዓት በላይ ወስዶ ሲያበቃ የመረጃውን ምንጭ ጠየቁት " ከራሱ የግል ማስታወሻ የተገኘ ነው" አላቸው፡፡

“እኛም እንየዋ ታዲያ” አሉት። “ጠይቁና ታዩታላችሁ” ብሎ ሊሄድ ተነሳ። ከመሰናበቱ በፊት ግን ሁለት ባለ መቶ ብር ኖት አወጣና ሰጠኝ፡፡ “ከኪስህ ቦርሳ የተገኘ ነው"

ይሔ ሰው በ 2005 የኔን መያዝ ተከትሎ የተካሔደውን የቤት ብርበራ የመራ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት መኮንን ነው፡፡ በዕለቱ የግል ማስታወሻዬን አንድ ጥራዝ ሼልፍ ላይ አግኝቷል፡፡ ከሚፈልግበት ጉዳይ ጋር የሚያገናኘው ነገር ያለ አይመስለኝም፡፡ ቢሆንም “ታይቶ ለቤተሰብ ይመለሳል” ብሎ ወስዶታል ። ቤተሰቦቼ ግን ተመላልሰው ማግኘት አልቻሉም፡፡ አንዴ “አስቀማጩ የለም” ይባላሉ፡፡ ሌላ ጊዜ “ነገ ኑና ጠይቁ” ይባላሉ። ሌላ ጊዜ ሌላ ቀን ይቀጠራሉ። በመጨረሻ እንደማይመለስ ተነገራቸውና መመላለሳቸውን አቆሙት። መርማሪዎቼም በተደጋጋሚ ጠይቀው እንዳልተፈቀደ ነገሩኝ፡፡

በሰኔ ወር 2010 ከእስር ቤት ተፈታሁ። የግል ማስታወሻዬን አንድ ኮፒ ሰው ጋር አገኘሁት። ይሄ ለንባብ እየቀረበ ያለዉ እሱ ነው። አንብቡት። የአላህን ስራ ታዩበታላችሁ፡፡

ወርቃማ ንግግሮች

02 Jan, 19:56


ሀዘንም ስለርሱ ያዝናል። ዓይንም ቋጠሮውን ፈቶ ያነባል። ደግመህ ደጋግመህ ብታለቅስም የእዝነት ነውና ይገባዋል። ስለኢስላም ዕንቅልፉን ሰውቷል። ስለ ከፍታ ዘመናችን እያለመ ሌቱን በቂያመለይል ያነጋል። እገሊት ተርባ ይሆን እስኪ ይህን ብር ስጧት ይላል። በአላህ መንገድ የተሰው ሰዎችን ቤተሰቦች አይዘነጋም። በባስ እየተጓዘ ስለነርሱ ምቾት ይጨነቃል።

ሰውነቱ ከሲታ፣ እዚህ ግባ የማይባል ስጋ ያልተላበሰ ቀጭን ረጅም። በቀን ትንሽ እንጂ የማይመገብ እንዲሁ ደገፍ ብሎ በጀርባው የሚጋደም። የሶማሊያ መንደሮች ጠንቅቀው ያውቁታል። ዛፎቹ በሚገባ ያስታውሱታል። እርሱ ግን መታወቅን አይፈልግም በኢኽላስ መስራትን ተክኖበታል።

ዕለቱ ሐሙስ እርሱም ፆመኛ ነበር። ከመስጂድ ወደ ታሰረበት ክፍል አመመኝ ብሎ አቀና። ፆመኛ ሆኖ አላህን ተገናኘ። መልካም ስራውን ተቀብሎ ኩልል ካለው የጀነተል ፊርደውስ ጅረት ያስጎንጨው ዘንድ አላህን እማፀነዋለሁ።


   Mahi Mahisho

ወርቃማ ንግግሮች

01 Jan, 06:14


🎁ታላቅ የሙሓደራ   ፕሮግራም📱


🅰️🅰️🅰️🅰️🅰️🅰️
🔤🔤🔠🔤🔤🔤🔤🅰️🔤  ግሩፕ  ላይ  የዳዕዋ  ፕሮግራም  አዘጋጅተን  እየጠበቅናችሁ  እንገኛለን።

ተጋባዥ 🔠🔠🔠🔠🔠🔠🔠🔠

⭐️ኡስታዝ ኸድር አህመድ
⭐️ኡስታዝ አብዱ ረዛቅ አል-ባጂ
⭐️ኡስታዝ ዶ.ሰዒድ ሙሳ
⭐️ኡስታዝ አቡ ሱፊያን
⭐️ኡስታዝ አቡ ሙአዝ
⭐️ኡስታዝ አቡ ዐብዲላህ ኢብኑ ኸይሩ
⭐️ሼህ አውል አል_ከሚሴ(አቡ አማር)

🔢መድረኩን የሚመሩልን ወንድሞች
አቡ ኹዘይፋ ሰኢድ
አቡ ሂበቲላህ ሁሴን
አቡ ፈዉዛን አብዱ ሽኩር

በእለቱም ታላቅ የምስራች ይኖረናል ሁላችሁም በጉጉት እንድትጠብቁን እናሳስባለን

❄️የፊታችን ጁማዓ✈️

ሰአት ⭐️ ከምሽቱ 3⃣:0⃣0⃣ጀምሮ

  ሙሓደራው  የሚካሄድበት  ግሩፕ
መርከዝ አቡ ፈውዛን🔤✈️🔤
    👇👇👇

t.me/merkez_abu_fewzan
t.me/merkez_abu_fewzan

ወርቃማ ንግግሮች

30 Dec, 12:37


≈ በአላህ ስም…

"የአላህን መስጂድ የገነባ ሰው አላህ በጀነት ውስጥ ቤት ይገነባለታል"

≈ ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው እኛ የጋምቤላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀምዓ በዋናው ግቢ (main campus) የሚገኘውን የመስጂዱን የቆርቆሮ አጥር በቡለኬት ለማጠር በእንቅስቃሴ ላይ ነን፡፡ይህን እንድናደርግ ካስገደደን ምክንያቶች ውስጥ የመስጅዱን ምንጣፍ እና የቆርቆሮ አጥሩን በየግዜው እየተዘረፍን ስለተቸገን መተካት የማንችልበት ደረጃ ላይ ደረሰናል።ስለሆነም አጥሩን በዘላቂ ግንባታ ለመገንባት አቅደናል።አሁን ላይ ባለን በተማሪ በጀት መገንባት ስለማንችል 50 በ50 ወይም 2500 ካሬ ሜትር ስፋት ባለው መሬት ላይ ለግንባታ የሚስፈልገን ወጪ ከአንድ ሚሊየን አምስት መቶ ሺ (1,500,000) ብር በላይ ስለሚያስፈልገን በያላችሁበት ሁናችሁ እንድታግዙን በአላህ ስም እንጠይቃለን፡፡

CBE:1000660517859

ወይም

CBO:1014100258727

Abdurezak Abdulkarim

And/or

Mohammed Umer

~ ለበለጠ መረጃ 0948184582 ወይም 0964588545 በዚህ ያግኙን።

የጋምቤላ ዩንቨርስቲ ሙስሊም ጀምዓ

≈ ሼር በማድርግ እንዲተባበሩን በአክብሮት እንጠይቀዎታለን።

ወርቃማ ንግግሮች

30 Dec, 03:09


╰ የተስፋ ገመድ….
。━━━━━━━━━━━━━━
▱ግማሽ ተምር ከጀሀነም እሣት የሚጠብቀን ከሆነ፣
▱ምጽዋት የጌታችንን ቁጣ የምታበርድልን ከሆነ፣
▱ዉዱእ ባደረግን ቁጥር ወንጀላችንን የሚረግፍልን ከሆነ፣
▱አላህን ስናወሳ አላህ የሚያወሳን ከሆነ፣
▱ወንድሞችን ስንዘይር መላእክት ዱዓእ የሚያደርጉልን ከሆነ፣
▱ሲዋክ አላህ (ሱ.ወ.) ዘንድ የሚያስወድደን ከሆነ፣
▱አንድ መልካም ሥራ በአሥር የሚባዛልን ከሆነ፣
▱መልካም ንግግር ምጽዋት ከሆነ
▱አላህን በጠረጠርነው ቦታ ላይ የምናገኘው ከሆነ፣


⎓…
⎓ታዲያ ለምን እንዘናጋለን …
⎓ከጀነት በብዙ ርቀት ላይ ነው ለነው ብለን ለምን እንሰጋለን! ወደ ጀነት ለመራመድስ ለምን እንፈራለን …. ⎓በሉ በተስፋ እንጓዝ 🌱….
⫸╯

ወርቃማ ንግግሮች

30 Dec, 02:52


ለሚስኪኖች ሰደቃ ስንሰጥ ከኪሳችን ውስጥ ትንሹን የገንዘብ መጠን ፈልገን እንሰጣለን … ከዛም አሏህን ፊርደውሰል አእላን እንጠይቃለን…

የስጦታችን ማነስ ከዛም የጥያቂያችን ትልቅነት… ይገርማል…

ሸኽ አሊ ጠንጣዊ

ወርቃማ ንግግሮች

30 Dec, 02:51


*የመጀመርያ ደረጃ ትምህርቴን ለመጭው ሂወቴ ስል ተማርኩኝ…
*ከዛም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትህን ለመጭው ሂወትህ ተማር አሉኝ…
*ቀጠሉና ሶስተኛ ደረጃ ትምህርትህን እንደዚሁ ለመጭው ጊዜህ ተማር ተባልኩ…
*ከዛም ለመጭው ሂወትህ ስራ ያዝ አሉኝ…
*ቀጠሉና ለመጭው ህይወትህ ስትል ትዳር ብትይዝ ጥሩ ነው አሉኝ…
*ከዛም ለመጭው ሂወትህ ልጆች ብትወልድ መልካም ነው አሉኝ…
*የሄው አኔ ዛሬ ይህን ፅሁፍ ስፅፍ የ 77 አመት ሰው ሆኜ አሁንም መጭው ሂወቴን ከመጠበቅ አልደከምኩም… *መጭው ሂወት ማለት ልክ እንደ አንድ በሬ ራስ ላይ ወደፊት ተደርጋ እንደታሰረች የሳር ዘለላ ማለት ነው እሷ ላይ ለመድረስ ይሮጣል ይደክማል ግን መቼም አይደርስባትም… ምክንያቱም መጭው ሂወቴ ብለህ ያሰብከውን ስትደርስበት ካለፎት የሂወት ጊዜዎችህ ጋር ይቀላቀላል ከዛም ደግሞ ሌላ የመጭው የሂወት ክፍለ ጊዜህን ለመቀበል ተጎዛለህ…

አውነታኛውና ትክክለኛው መጭው ሂወትህ ማለት…
አሏህን ስታስደስት ከእሳቱ ተጠብቀህ ጀነት መግባት ስትችል ብቻ ነው …

ሸኽ አሊ ጠንጣዊ ረሂመሁሏህ

ወርቃማ ንግግሮች

29 Dec, 15:01


ሩሲያ ውስጥ ያለ ህክምና ነው ። ይህ ህክምና መድሀኒት ሚሰጠው የወሲብ የመጠጥ የሀሺሽ የሌሎችም እፆች ሱሰኛ የሆኑትን ነው ። ህክምናውም ሚሰጠው ጀርባን በደንብ በመግረፍ አእምሮን ካለበት ስጋዊ ሱስ ነፃ እንዲወጣ ማድረግ ነው ።

ወደቁምነገሩ ስንገባ ..
ውዱ ዲናችን የዝሙተኛ ግርፊያ 100 የመጠጥ ጠጪን ደሞ 80 ጂራፍ ያደረገበት ሚስጥር ለቅጣት ብቻ ሳይሆን .. ውስጡ ያለው ከባእድ ሰው ጋ መዋሰብን ከአእምሮው ለማስወጣት የእፅ ሱስንም ፍቆ የማውጣት አቅም ስላለው ነው !

እንደሚታወቀው ከሺርክ ቀጥሎ ትልቁ ወንጀል አንድ ሰው በማይፈቀድለት ማህፀን ውስጥ የሚያሳርፈው ፍትወት ነው ።
ከ7 አጥፊ ወንጀሎች ውስጥ ኸምር መሆኑም እንዲሁ ግልፅ ነው ። ለነዚ ከባባድ ሱሶች እና መጫረሻ የሚያበላሹ አደጋ ነገሮች መፍትሄው እና ቅጣቱን ሸሪአ ማበጀቱ ድንቅ ነው ።
الحمد لله على نعمة الإسلام

Jabir Mustefa

ወርቃማ ንግግሮች

28 Dec, 18:06


በዓለማችን ታዋቂውና የተሻለ የሚባለው የእንግሊዝኛ ቁርኣን ትርጉም Sahih International ሲሆን የተዘጋጀውም በ3 ሰለምቴ አሜሪካውያን ሴቶች ነው።

♦️የመጀመሪያዋ ❝ኤምሊይ አሳሚ❞ ወይም አሚናህ ዑሙ-ሙሐመድ ትባላለች። የተወለደችው ካሊፎርንያ ሲሆን ቤተሰቦቿ እምነት የለሾች ናቸው። ኢስላም ሴቶችን እንደሚጨቁን ስትሰማ ለማጣራት ቁርኣንን ማንበብ ጀመረች። ከዚያ በወቅቱ በአሜሪካ በቂ የኢስላም መጽሐፍ ስላልነበሩ ወደ ሶርያ በመሄድ ከደማስቆ ዩኒቨርስቲ ዐረቢኛን አጥንታ ክሱ ቅጥፈት መሆኑን ስታረጋግጥ ኢስላምን ተቀበለች። ከዚያም በ1981 ወደ ሳዑዲዓረቢያ ሄደች።

♦️ ሁለተኛዋ ❝ሜሪ ኬኔዲ❞ የተወለደችው በኦርላንዶ ሲሆን የእንግሊዝኛ ቋንቋ ምሩቅ ናት። ቤተሰቦቿ ክርስቲያኖች ናቸው። በኋላም ወንድሟ ኢስላምን ሲቀበል በእሱ ምክንያት በ1985 ኢስላምን ተቀበለች። ከዚያም በ1987 ወደ ሳዑዲዓረቢያ ሄደች።

♦️ ሶስተኛዋ ❝አመቱላህ ባንትሌይ❞ ስትሆን የካቶሊክ እምነት ተከታይ የነበረችና ከሚኒሶታ ዩኒቨርስቲ የቢዝነስ ማኔጅመንት ምሩቅ ናት። የሰለመችው በ1986 በዓለምአቀፍ የሙስሊም ተማሪዎች ማህበር አማካኝነት በ20 ዓመቷ ነው። ከዚያም በ1987 ወደ ሳዑዲዓረቢያ ሄደች።

👉 በ1990 አካባቢ በሳዑዲ ሳሉ በአጋጣሚ ተገናኝተው ተዋወቁ። በዚያው ሰሞን ሙስጠፋ የተባለ ሰው ቁርኣንን በቀላል እንግሊዝኛ ለመተርጎም ጀምሮት እንደሞተ ሲሰሙ ስራውን ለመጨረስ ተነሱ። በዚህም ከዚያ በፊት ፍፁም አስበውት የማያውቁትን የቁርኣን ትርጉም በ1994 ጀምረው በሶስት ዓመቱ በ1997 አጠናቀቁት።

በኋላም መጽሐፉ በዓለም ላይ ቀላሉና የተሻለው የእንግሊዝኛ ትርጉም ለመሆን የበቃ ሲሆን ሶስቱም በህይወት በመኖራቸው የስራቸውን ፍሬ ለማየት ታድለዋል። ዑሙ-ሙሐመድ ኤምሊይም ከዚያ በኋላ ከ80 በላይ ኢስላማዊ መጽሐፍት አዘጋጅታለች። እነዚህ እህቶችም ኢስላም በቁርኣን ጭምር የሴቶችን እውቀት የሚተማመን መሆኑን ማሳያ መሆን ችለዋል።

ወርቃማ ንግግሮች

26 Dec, 11:13


ስለ ቴሌግራም 🫣😮😕😕😄😓
ጥቅም በሰፊው ለማወቅ

t.me/abdu_tech_1/5

🔤🔤🔤 business (online )
        ስራ  ለምትሰሩ የቴሌግራም
😮😕😕😄😓 ጥቅም  ለማወቅ

t.me/abdu_tech_1/7

ቴሌግራም አካወንታችሁ
😮😕😕😄😓
ለማስደረግ ለምትፈልጉ


t.me/abdu_tech_1/13
t.me/abdu_tech_1/13

ወርቃማ ንግግሮች

23 Dec, 16:39


ትናንት አንድ ወንድም ጋር ተጨዋወትን። ፋርማሲ አለው። የኡማው ነገር እጅግ እጅግ አስጨንቆታል። እንደሱ አባባል "ዚና ከሚገባው ላይ ቀውማችን ጋር ተስፋፍቷል፣ በርካታ የኛ ቀውም ቪያግራ፣ ድህረ ዚና እርግዝና መከላከያ (post 💊)፣ ኮንዶምም ይጠይቁኛል ምን ይሻላል። ኮንዶም እኔ ሱቅ አልሸጥም" አለኝ። ከዚህ አልፎ የነገረኝ ነገር በሙሉ ይዘገንናል።

እኔም ይሄን መከርኩ👉 ኮንዶም ሽጥላቸው፣ ቢያንስ ለተውበትም መኖር ይፈልጋልና ቢኖሩ ይሻላል።

ከተቻለ እንደውም ኮንዶም የምትሸጡ ሰዎች ስለዚና ክፋት ፓንፕሌት አዘጋጅታችሁ አብራችሁ ስጧቸው።

ቪያግራ ከ30 አመት በታች ለሆነ ሰው አትሽጡ ። ፊቱን አይታችሁ ያላገባ ሰው ከሆነ ዚናን አታጣፍጡለት። እዛው ከነ ፓራሊሲሱ ይንደፋደፍ።

ከዚና በኋላ የሚሰጠውን ፒልስን በተመለከተ አሊም ጠይቅበት። እንደኔ ቢሸጥላቸውና ቢጠቀሙበት ይሻላል...ተረግዞ እናስወርዳለን ብለው እንዳይሞቱ.. ያው ከነኺላፉ ሩህ አልተፈጠረበትም ብየ የደሩሪ ወሬ አወራሁ። ፈትዋ አልሰጠሁም። አሊም ጠይቁበት...መገን ፈተና።

ዚና ቀርቶ ኢህቲላጥ ነውር የሆነበት የምስራቅ ኢትዩጵያ ላይ እጅግ በአስደንጋጭ ሁኔታ ዚና ተስፋፍቷል። ዛሬ ላይ ልጆቻችን በዳንስ ቤት ተቀላቅለው ሲደንሱ መታየት በቲክቶክ መልቀቅ ምንም የማይመስልበት የቅድመ አረብያ ቀውም መስለናል።

ሁላችንም በሽተኛ ነን። መዳኒት ሰጭም የለም። አብረን ለመዳን መወሰን እናም መዳኒቱንም ለማግኘት ህመማችንን አውቀን መታገል አለብን።

በዚህ ጉዳይ በየከተማው ጠንካራ የሴቶች ለሴቶች ማህበራት መቋቋም አለባቸው። ሀሳብን ልምድን ቢጋሩ እጅግ ይጠቅማል። የወጣቶች ማእከላት በየመስጅዱ ያስፈልጋሉ። እህቶች ተጠንቀቁ 👉 ሁሉም ዛኒ ወንድ በላውን ሁሉ እናንተን አሸክሞ ዘወር ይላል ..ሊያገባ ሲወስን ቢክራ ይፈልጋል። ዛኒ ወራዳ ሰው ነው። እህቶች ራሳችሁን አድኑ ተመካከሩ።

አድበስብሰነው እንደ ምርጥ ባሪያ አክት እያደረግን ከዚ በላ መውጣት አንችልም። በየደረጃው መነጋገር አለብን። ምን ይሻለናል?


☞ Kha Abate

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 19:24


የሰው ልጅ እንደ እፅዋት ቅጠል ይረግፋል አልፎ ተርፎም እድገታቸው ሆነ መባቻቸው አረጓዴ ቢጫ ሆነው በመጨረሻም ከመሬት ይዘረራሉ።

ህይወትም ሆነ የዚህ ዓለም ስርአት ይሄው ነው። ግን የሰው ልጅ ከፍጥረት ሁሉ ልቆ እንደተፈጠረም ሁሉ የህወትን ዓላማ ኖረ ሞተ በሚለው አይቆጭም። የሰው ልጅ የተፈጠረው አላህ በመገዛት እና ከሱ ውጭ ባለው መካድ ነው።

~ Ibnu Mohammed

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 10:02


ይህ የተኖረ እውነተኛ ህይወት ነው።
ባለ ታሪኩ ደሴ ዙሪያ የኩታበር ልጅ ነው።
ስሙ አቡ ሂላል በፌስቡክ መጠሪያው ነው።

ጀዛኩም አላህ ከይረን።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 10:01


☔️ወደ ቀሶሳችን☔️

✍️አንዳንዴ ድክም ምርር ሲልህ ይህ ለምን ሆነ የሚል ወስዋስ ዐቅልህ ላይ ሽው ይልብሓል ነገር ግን ወደ ቁርኣንና ሐዲስ ፊትህን ባዞርክ ጊዜ መሰረታዊና ጦመእኒና የሚፈጥር መልስ ታገኛለህ።
፨ለምን ታሰርኩ ስትል ዱኒያ ለሙእሚን እስርቤት እንጅ ሌላ መች ሆና ታውቃለች የሚል መልስ ታገኛለህ።

✍️እስርቤት መጥፎ ነው።በእረኞች የምትጠበቅ ሰው ትሆናለህ። የእስር ቤቱ ግቢ የኳስ መጨዋቻ ሜዳዋ ላይ ሰውነትህን በወክ እያፍታታህ ባለህበት ቅፅበት ነው እኮ ልክ ሊመሽ አካባቢ ፀሓይ ልትገባ በተቃረበች ጊዜ ግው ግው የሚል የበር ድምፅ ትሰማለህ።ቆጠራ ቆጠራ የሚል ድምፅ በሚኒሚዲያው ይነገራል።ሁሉም በየማጎሪያው በር ጥንድ እየሆነ ይሰለፋል።የማረሚያ ቤቱ እረኞች እየቆጠሩ ያስገቡንና በሩን ክርችም አድርገው ቆልፈውት ይወጣሉ።
✍️ተመልከት በሩን መክፈት አትችልም።በሩን መክፈት እንደማትችል ስታውቅ የስነልቦና ሕመም ያምሓል።
✍️በሩ ተቆልፏል ለይል ብትታመም በር እየወገርክ ድረሱልን ብሎ እረኞቹን ከመጣራት በስተቀር ሌላ አማራጭ የለህም።
✍️እኔ የነበርኩበት ዞን 3 ማለት እኔ በብልፅግና ጊዜ ስታሰር ከእኔ ቀድመው በወያኔ ጊዜ የታሰሩ የድምፃችን ይሰማ ታሳሪ ሙስሊሞች በብዛት የነበሩበት ዞን እንደሆነ በተደጋጋሚ የሚታሰሩ ዱርየዎች ነግርውኛል።
✍️ቂሊንጦ ዞን 3ከታሰሩ የድምፃችን ይሰማ ታሳሪዎች መካከል የደሴው ጀግና ሙባረክ ይመር رحمه الله ይገኝበታል።
✍️ሙባረክ رحمه الله ለይል ነበር የታመመው አሉ።መክፈት የማትችለው በር ተከርችሞ ወንድምህ ደግሞ በሕመም እያጣጣረ መመልከት ግን እስኪ ከሕሊናችሁ ጋ አስተውሉት✍️ሙባረክ ሆዱን ነበር በጣም የታመመው።እስረኛው የጉረናውን በር በሓይል እየወገሩ ድረሱልን ቢሉም ጥጋበኛው የወያኔ የቂሊንጦ እረኛ ግን ሰምቶ እንዳልሰማ ሆነ።በዚህ መካከል ሙባረክ ሕመሙ በጣም እየጠናበትና እያዳከመው ነበር ወንድሞቹም በሩን በሓይል እየመቱ ቢጮሁም ፖሊሶቹ የደረሱት በጣም ዘግይተው መጡና ምንድን ነው ሲሉ ወንድሞቹ ሰው ታሞብን ነው በማለት ነግረዋቸው በሩ ተከፍቶ ፖሊሶቹ ገብተው ሙባረክን ወደ ሕክምና ለማድረስ ማነው የሚደግፈው አሉ።
✍️ታውቃለህ እስርቤት ቤተሰቦችህ የሉም ፣የቅርብ ጓደኞችህ የሉም።ስትታመም የሚያስታምምህ ስታለቅስ እንባህን የሚጠርግልህ የለም።እዛው እስርቤት ያሉ ሰዎች ናቸው ይህንን ሁሉ የሚያደርጉልህ።
✍️ሙባረክ ግን አብረውት ጎደኞቹ አሉና ተሸክመው ሕክምና ቢያደርሱትም አላህ የፈለገውና የመረጠው ሆኖ ወደ አኼራ ሄደ።رحمه الله وغفر له

✍️አስተውል እስኪ አብሮህ የታሰረ ሙስሊም ወንድምህ እዛው እስርቤት ውስጥ ስታጣው😥
✍️ሙባረክ ጀናዛው ደሴ በገባ ጊዜ እጅግ መሪሪ ሐዘንና ቁጭት ነበር የፈጠረብን። የሙባረክን ጀናዛ አጂበን ወደ ቀብር ቦታ ሄደን አሳረፍነው። አላህ በጀነት ያሳርፈውና።
✍️ሙባረክን ቀብረን ስንመለስ ከቦንቧ ውሓ ደሴ አራዳ የደረሰ የወንድሞቹ የቁጣ ማዕበል ተጥለቅልቆ ነበር።በመጨረሻም በርካታ መከላከያ ጦር ጢጣ መሽጓል ተበተኑ ሁሉም ወደመጣበት ይመለስ የሚል ትዕዛዝ ጥቅምናጉዳቱን ከሚለዩ ሽማግሌዎች በተሰጠን ጊዜ በቁጭት ሁሉም ወደቤቱ በሰላም ተመለሰ።

✍️ያኔ የወያኔ ተቀናቃኝ ኢሳት በየት ቪድዮውን እንደቀረፀው ባላውቅም እረ አንተ ኢሳት ላይ አየንህ ተደበቅ የሚል ስልክ ከየቦታው እየተደወለ አዛ አድርጎኝ ቤተዘመድንም አስጨንቆ ነበር። አላህ የእኔን መታሰር በወያኔ ሳይሆን በብልፅግና ዘመን ነበር የወሰነውና በጊዜው ምንም አልሆንኩም።

✍️ሙባረክ ባለቤቱንና 2 ልጆቹን ለዚህ ኡማ አማና ሰጥቶ ነው ወደ አኼራ የሄደው። 😥እኛ ግን

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 10:00


☔️ወደ ቀሶሳችን☔️

✍️የፌደራል አቃቤ ሕግ ምስክሮች ጋ ፍጥጫ
፨ባለፈው እንደነገርኳችሁ ጉዳዩ
لا يُرفَع البلاءُ إلا بتوبة
ነውና ነገሩ ይህ ቀጠሮ ቀኑ በቀረበ ጊዜ ራሴን በጣም ሰብሰብ አድርጌ ተገለልኩኝ። የማስታውሳቸውን ትልቅም ትንሽም ሓጢያቶቸን እያስተዋልኩ አላህን ምህረት መጠየቄን ተያያዝኩት።የማስታውሰውንም የማላስታውሰውንም ግልፁንም ድብቁንም ወንጀሌን ማረኝ ማለትን አዘወተርኩ።👉በእኔ ላይ ሊያደርጉ ያሰቡትን ሲህራቸውን ሁሉ በራሳቸው ላይ አድርግባቸው ማለትን የሙጥኝ አልኩ።
✍️ምክኒያቱም አላህ እንደዚህ አይነት ሙሲባዎችን ለባሪያው የሚያመጣቸው አደብ ለማስያዝም ጭምር ሲሆን ገለል አድርጎም ለእርሱ በኢኽላስ ዒባዳ ያደርግ ዘንድም ነው።
إنما جُعِلَت العلل
ليؤدب الله بها العباد
ይላሉ አንጋፋው ፉደይል ቢን ዒያድ رحمه الله
✍️የአቃቤ ሕግ ምስክር ቀረበና እኔ እከሌ የእከሌ ልጅ በሐቅ ልመሰክር በአላህ 🙄ስም እመሰክራለሁ በማለት ቁርኣን ላይ እጁን አደረገ።አላህ አላህ ኢስላማዊ መንግስት ሊመሰርት ተብዬ በታሰርኩት እኔ ላይ ኢስላምን በመረጠልን አላህ ስም ምሎ ሊመሰክርብኝ 😥
✍️ችሎቱ ስርዓቱን ጠብቆ ተሰይሟል።የእኔ ጠበቃ ግን አልመጣምና ዳኞቹ መስቀለኛ ጥያቄ መጠየቅ ትችላለህን አሉኝ እኔም አወ እችላለሁ ብዬ ራሴን አዘጋጀሁ።
✍️ይህ ምስክር ቤቴ ሲፈተሽ የነበረ ፌደራል ፖሊስ ነው።
✍️አቃቤ ሕጉ ምስክሩን ማናገር ጀመረ ምስክሩም አወ ቤቱን ስንፈትሽ የሽብር ዶክሜንት የያዙ ፍላሾችንና ሌሎች ነገሮችን አግኝተናል በማለት ቃሉን ሰጠ።ክላሽ ቢያገኙ ምን ሊሆኑ ነበር በፍላሽ ይህ ሁሉ😂😂
✍️ተራው ለእኔ ደረሰና የምጠይቀው ካለህ ብሎ ችሎቱ ፈቃድ ሰጠኝ።እኔም የአቃቤ ሕግ ምስክር ፉላን
፨እነዚህ ቤቱ አገኘናቸው ያልካቸው እቃወች እኔ ቤት ለመገኘታቸው በዐይንህ አይተሓልን?ከምንስ ላይ ነው እቃዎቹን ያነሳችሁት?አንተስ ቤት ውስጥ ፍተሻው ላይ ነበርክን?በማለት ስጠይቀው
ቆጣ ብሎ😂
✍️እኔ ቤት ውስጥ አልገባሁም አለ😂ትልቅ ማኖ
ዳኛው ቀበል ብሎ ታዳ ቤት ውስጥ ካልገባህ እንዴት አይቻለሁ በማለት ትመሰክራለህ ሲለው
ንደቱ እየጨመረ ነው 😂እኔ በር ላይ ጥበቃ ላይ ነበርኩ ፍተሻ የገቡ ሌሎቹ የፀጥታ አባላት በእጃቸው ይዘው ሲወጡ ነው ያየሁት ሲል
✍️ዳኛው ቆይ ቆይ ከምን ላይ ሲነሱ ሳታይ እጁ ላይ ሳታይ ሌሎች ወታደሮች ይዘው ሲወጡ ስላየህ ብቻ
ምናልባት እነዛ ወታደሮች ይህንን ልጅ ለማሳሰር ራሳቸው ያዘጋጁት ዶክሜንት ቢሆንስ 😂ሲል ዳኛው
✍️አቶ ምስክር ነቀሉ ጨርሰው እንዴት እንደዚህ ሊሆን ይችላል ብሎ ከችሎቱ ጋ ሲፋጠጥ ችሎቱ ስነስርዓት ይኑርህ ሊሆን ይችላል በሚል ነገር አይቻለሁ ተብሎ ቃል አይሰጥም አሉት።
انقلب السحر على الساحر
ሆነ መሰል ነገሩ።
✍️በዚህ መልኩ ችሎቱ 2ኛ እና 3ኛ ምስክርን ለመስማት ሌላ ቀጠሮ በመስጠት ችሎቱ ተጠናቀቀ።.......

✍️ይህ ቀሶስ ይህን የሚፅፍላችሁ የእኔው የአቡ ሒላል ነው።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 10:00


☔️ወደ ቀሶሳችን☔️

✍️ከሞባይሏ መወሰድ በላይ እኔ ላይ ቦክስ መሰንዘራቸው ግጭቱን ሊያባብሰውና ሌላ መስመር ሊይዝ ነበር ነገር ግን እነዛ የፊት ጥርስ የሌላቸው የድሮ አራዳ እነ ናደው 😂እንደምንም ለማረጋጋት ሞከሩ። ይህ ሁሉ ሲሆን
✍️የአክተሮቹ አክተር ብለው የሚጠሩት ወሎዬው ማሜ ከጀርባ ከጓደኞቹ ጋ ወክ እያደረገ ነበር። የሚገርመው ጓደኞቹም
✍️እኔ ከጉራጌ ፈሪ ቢገኝብኝ
ሞት ይፈረድብኝ የሚሉ ደፋሮች ነበሩ 😂😂
✍️ወሎዬው ማሜ ፌደራል ነበር።በዚሁ ስራ ላይ እያለ ነው የባጀት ብር ዘርፋችሗል ተብሎና ሌላ ተጨምሮ በ2ክስ የታሰረው።
✍️ያኔ የትግራይ ወጣቶች እየተለቀሙ የሚታሰሩበት ወቅት ነበርና ግቢው ውስጥ የሓይል ሚዛን እየፈጠሩ ነበር ቢሆንም ግን ከወሎዬ ጋ ማንም አይጋጭም ለዛውም የጀመዓው ኢማም ስትሆን 😂
✍️እንደምንም ቅዳሜ እየመሸ ነውና የማታ ቆጠራ ተቆጥረን በየማጎሪያችን ገብተን እንደተለመደው በር ተቆለፈብን።
✍️ማሜ እና እኔ የተለያየ ቤት ነንና ተቆጥረን እንደገባን እሱ ቤት ያሉት ልጆች የተፈጠረውን ግጭት ሲነግሩት አጅሬ በንዴት ጭሷል ኡፍፍ እያለ እሳት ሲተፋ ያድራል።ኸይርነቱ ያን የሰሩት ልጆችም ሌላ ቤት መሆናቸው ጠቀማቸው።
✍️ለይሉ ነጋና እሁድ ጧት በር እንደተከፈተ ማሜ ከጓደኞቹጋ ወደ እኔ መጣና ልጆቹን አሳየን ዛሬ ደም መፋሰስ🙄አለብን እያሉ በቁጣ ነገሩኝ።እኔም እረ ቆይ ተረጋጉ በዚች በማትረባ ስልክ ደም ለምን ይፈሳል።የወሰዱት ልጆችም የዱሮዬ እልህ ይዟቸው ነው እንጅ ይመልሳሉ እያልኩ ለማረጋጋት ሞከርኩ አይ አንተ የዱርየውን ተንኮል አታውቀውም ዛሬ ሁሉም ነገር ይለይለታል እያሉ መደንፋት ዋይእ😂
✍️ሁሉም እንደብሔሩ ጥግጥጉን ይዞ ፀሓይ እየሞቀ ሴራ ይሸርባል። ቅዳሜና🙄 እሁድ ወደ ግቢ ብቅ የሚል ሹርጧ ስለለ አስቸጋሪ ነው።
✍️ልጆቹን ስልኩን መልሱ ሲባሉ ሌላ ግቢ ወርውረነዋል አሉ። ከዞን ዞን ባየና ሲጋራ በእንጀራ ጠቅልለው በፌስታል ታስሮ ነው በውርወራ የሚቀባበሉት።
✍️ጉዳዩ ወደ ብሔርም ወደ እምነትም ሊዞር ይችላልና አስፈሪ ነው። ድባቡ ያስፈራቸው በእድሜ ገፋ ያሉ ታሳሪ ሽማግሌዎች ጣልቃ ገቡና አሸማገሉ።እኔም አንዳንዴ ሲነካ በዝምታ የማታልፈው ክብር አለና ስልኳን ካላመጡ ስምምነት የለም አልኩኝ። ልጆቹም እልሓቸው ተንፍሶ ስልኳን መለሱ እሁድ ከሰዓትም በሰላም አለፈ።
✍️ይህን ሁሉ ሲከታተል የነበረ በሙስና የታሰረ ግቢው ውስጥም አስጠጭ በመሆን አዛ ያደረገን ካቦ ሰኞ ጧት እኔ መሕከማ ከሄድኩ በሗላ ቅዳሜና እሁድ የተፈጠረውን ግጭት ልቅም አድርጎ ፅፎ ለዞን ተጠሪ ፖሊስ አስጠጥቷል🙄
✍️ስሜን ጠቅሶ ስልክ ተወስዶበት የሓይማኖት ፀብ ሊያስነሳ ወዘተ ብሎ ስልክ የወሰዱትንም ልጆች ስም ዝርዝር ተናግሯልና ከመሕከማ ስመለስ በቁጣ ቁም ሸሁ ያለኝ ፖሊሱ ለዚህ ነው ለካ
✍️እኔ ነው ስል አወ አንተን ነው ደግሞ ግቢው ውስጥ ያለው ደህና ሰው እሱ ነው እንላለን አንተ ግን ግቢውንም ታሸብራለህ😂አለኛ።ስልክ ወሰዱ የተባሉትንና የጀመዓችንን ሙዓዚን ጧት ጀምረው በካቴና ጠርንፈው ፀሓይ ላይ አስጥተዋቸዋል 😂 አይይ መከራ እኔ እስክመጣ እየተጠበቀ ማለትኖ።
✍️ዞን ተጠሪ ቢሮ ገባንና በዚህ ሁለት ቀን ረብሻ ልታስነሳ ነበር እነሱ ስልክ ወስደውብሓል ተጣልታችሗል እያሉ ሲያፋጥጡን እረ ስልክ የለኝም በየት ገብቶ እነሱም ጋ አልተጣላሁም ብዬ ግግም ነዋ😂እንኳን ለእናንተ ለFBiም ሚስጥር አላወጣን አልኩኝ በሆዴ ነው ታዳ
✍️ዞን ተጠሪው በንዴት በቃ ሰብስባችሁ ቅጣት ቤት አስገቡልኝ እዛ አይጥ ጋ ይፋጠጡ አለ 😥 በስንት ልመና ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ጋ አስፈርመውኝ ወደ ማጎሪያችን።الحمد لله

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 10:00


☔️ወደ ቀሶሳችን☔️

✍️ለችሎቱ ንፁህነቴን ፣ክሱ ሐሰተኛ ክስ እንደሆነ ለማስረዳት በምሞክርበት ችሎት ላይ በግራ በኩል የተቀመጠው ዳኛ በሹፈት እንድህ አለኝ ፦ክሱ ሐሰተኛ አንተም ንፁህ ከሆንክ የደህንነት መረቡ ለምን አሰረህ ?አለኝ
✍️እኔም ሙስሊም ስለሆንኩ ነው የታሰርኩት በማለት መልስ ሰጠሁ።እህ እዚች አገር አንተ ብቻ ነህ ሙስሊም የሚል ጥያቄ ተከተለ
✍️አይ እኔ ብቻ አይደለሁም ነገር ግን ከእኔ በፊት የታሰሩ ነበሩ ወደፊትም ተራ የሚጠብቁ አሉ 😂በማለት ሹፈቱን ወደ ብስጭት ቀየርኩለታ
✍️የተመደበው ጠበቃም በተወሰነ መልኩ ለመከራከር ከሞከረና ዳኞቹም መልስ እየሰጡ ደቂቃዎች ከቆየን በሗላ አቃቤ ሕግ የሰው ምስክር አለኝ ብሎ ስላቀረበ ቀጣይ ቀጠሮ ላይ የአቃቤ ሕግ ምስክሮችን ቃል እንሰማለን በማለት በቀጠሮ ወደ ደያሴና ቂሊንጦዬ ተመልስኩ።
✍️ከልደታ መሕከማ ቂሊንጦ ማጎሪያቤት ደርሸ ካቴናው ተፈቶ የተለመደውን ፍተሻ አድርገው ወደ ዞኔ ልገባ ስል
✍️በንዴት በጦፈ ድምፅ ሸሁ ቁም 🙄 የሚል ድምፅ ሰማሁ ሸይኾች የሌሉበት ቦታ ተገኝቸ ሸይኽ ተብዬ የምጠራው ግቢው ውስጥ እኔ ብቻ ነኝና ዘወር ብዬ እኔን ነው ስል አወ አንተን ነው አለኝ የዞን ተጠሪው አለቃ አበራ 😂
✍️ይህ የሆነበት ምክኒያት ሰኞ መሕከማ ልቀርብ ወደሗላ ቅዳሜና እሁድ ግቢ ውስጥ ትንሽ conflict ተፈጥሮ ነበር። ግጭቱም አንድ ሸገር የሚኖር የወሎ ተወላጅ ባለሓብት በሕገወጥ መሳሪያ ዝውውር ታስሮ እኛ ግቢ ነበር። በመርከበኛ ሞባይል ይገባልና እርሱም አስገብቶ ነበር።በእርግጥ Jx በተን ስልክ እዛ ስትገባ ከ3ሺ እስከ 5ሺ ድረስ ትፈጃለች😂ለባቡሩ ማለት ነው አላህ አላህ
✍️እናም ይህ ወንድም አንተ ቤት ቻርጅ አድርግልኝ ብሎ ሰጥቶኝ ቲቪው ጋ ቻርጅ ተሰክታ እኔ ውዱእ ለማድረግ ወደ መታጠቢያ ክፍል በገባሁበት ቅፅበት ከቅጣት ቤት አዲስ የመጡ ወመኔዎች ስልኳን ነቅለው ወሰዷት።ጠብቁ ያልኳቸው ልጆች ተው ሊሏቸው ሲሞክሩ አንዱ ወዲይ ነውና ዋይእ ኣተ ዚሞበል በማለት ሲያፈጥባቸው ፈርተው ዝም አሉና እኔን እረ ኡስታዝ ስልኳን ወሰዷት አሉኝ።ማነው የወሰደው ስል እያቸው እዛ ቴንስ መጫወቻው ጋ ወክ የሚያደርጉት አሉኝ። ወመኔዎቹ 3ናቸው 2ቱ በነፍስ የገቡ ናቸው አንዱ ደግሞ ቀስቴ ነው 😂
✍️እኔ የዋህ ወንድማችሁ ምንም ሳይመስለኝ ሽርጤን እንደለበስኩ ሒጄ ለምንድ ነው ስልክ የወሰዳችሁት ስላቸው አንዱ ወዲው በታቶ የተዝጎረጎረው ዞር በል ብሎ ወያሎች የሚሳደቡትን ስድብ ሰደበኝ😡
✍️ስድቡን አልወደውምና በጣም የሌለ ቱግ አልኩ በእርግጥ የሚወደድ ስድብ የለም። አንተ ማን ስለሆንክ ነው እኔን የምትሳደበው ስልኩን አምጣ ብየ ጠጋ ስል በአንድ ቦክስ ሰው ገድሎ የታሰረው ወመኔ ሐይለኛ ቦክስ ሲሰነዝርብኝ እንደምንም ለመከላከል ሞከርኩ ትንሽ ቢያገኘኝም ግን አልተጎዳሁም። ሌላዋ ቀስቴ ወመኔ ጓደኛቸው ተንደርድሮ በምላጭ ሊመርሸኝ ሲል ገራገሩ ወሄ ጓደኛዬ ዐብዱልወኪል አላህ ይቀበለውና እጁን ይዞ ተረፍኩ።ወመኔዎቹ ቁጥራቸው እየጨመረ መጣ።የግቢው አክተር የሚባሉት ናደው ግብዳው የሚል ስያሜ የተሰጣቸው የፊት ጥርስ የለላቸው 😂ወመኔዎች ተኝተው ነበርና ልጆች በሰቀሷቸውና እየሮጡ መጡ። ግቢው ቀውጢ እየሆነ ነው አንዱ ናደው በቃ አንተ ቤት ግባ እኛ እንጨርሰዋለን በማለት እነዛ ቀማኛ ወመኔዎችን እናንተ እንዴት እንደዚህ ትሰራላችሁ ሙሀመድ ቢሰማና ቢኖርኮ ተጨፋጭፈን ነበር በማለት ተቆጧቸው።ወመኔዎቹም ይህ ልጅ ምንድን ነው አክተሮቹ ሳይቀር የሚወግኑለት በማለት ደንገጥ ብለዋል።
✍️ሙሀመድ ማለት የወሎ የኮቻ ልጅ ነው።የአክተሮቹ አክተር ጀግና ስፓርተኛ ልጅነው።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 09:59


☔️ከቀሶሳችን አጋጣሚዎች ☔️

✍️በዚች ዱኒያ ውስጥ ሰው በሞላበት ምድር እንግዳነት ከባድ ነው።እንግዳነትህን የማይረዱ ሰዎች ደግሞ የበለጠ በእንግዳነትህ ትፈራለህ።
✍️መሪር እንግዳነት የሚሰማህ ደግሞ እስርቤት ነው።በወታደሮች ወከባ ለእስር ተዳርገህ ስትገባ።አገሩም ፣ሕዝቡም ፣ቋንቋውም ለአንተ እንግዳ ሲሆንብህ አስበው።
✍️የመኒ ነው።ሒላል ወሊድ ይባላል። አጠር ያለ ፀጉሩ ቀይ መልከመልካም ጎልማሳ ነው። አገሩ የመን በጦርነት ቀውስ ውስጥ ስትገባ ሙሉ ቤተሰቡን ማለትም ሚስቱንና ልጆቹን ይዞ ወደ ኢትዮጲያ አዲስአበባ ገብቶ ኑሮውን ጀምሯል። ነገር ግን ስደተኛ ሆኖ የሚሰራውም ለልጆቹ ቀለብ መሸመት ሲከብደው ወደ ጆርዳን ለመጓዝ ቦሌ ኤርፖርት በገባ ጊዜ ነበር ሕገወጥ እቃ ይዘሓል በማለት በቁጥጥር ስር አድርገው እያጣደፉ ፖሊስ ኮሚሽን ያመጡት።
✍️የመኒዎች ደግ ሕዝቦች ናቸው። የመኒዎች ለነገ የሚያስቀምጡት አላህ ከሪም የሚለውን ታላቅ ቃል ነው።ከሪሙም አላህ አይተዋቸውም። የመኒዎች የተወደዱ ሕዝቦች ናቸው።
የመኒዎች
قال الإمام ابن تيميّة رحمه الله:

ْالرِّضَا

جَنَّةُ الدُّنيَا،

وَمُسْتَراحُ العَابِدِينَ،

وَبابُ اللهِ الأَعظَم.

مجموع الفتاوى (٢٧/١٧)
የሚለውን ቀውል በሐቂቃው የሚኖሩ ናቸው።
✍️ሒላል ፖሊስ ኮሚሽን አምጥተው ባስገቡት ጊዜ የውጭ ዜጎች የሚመደቡት ክላስ ነበር ከናይጀሪያዎች ጋ ያስገቡት።
✍️የዝሁር ሶላት ሰግደን ስንጨርስ ወደ ጀመዓው ዘወር ስል ከመጀመሪያ ሶፍ ላይ ሆኖ በባይተዋርነት አይን እያየኝ ጠጋ አለኝና
👉هل انت يمني ብሎ ጠየቀኝ
የመኒ ስለመሰልኩ ደስ ቢለኝም😍 እረ የመኒ አይደለሁም ሐበሻ ነኝ አልኩት።
✍️ያለበት ክላስ በሐሺሽ አዋዋሪነት የታሰሩ ናይጀሪያዎች ነበሩና እንዳልተመቸው ከእኛ ጋ መሆን እንደሚፈልግ እያስተዛዘነ ነገረኝ።እኔም እዛች ግቢ ስገባ የተሰማኝን ባይተዋርነት አስታወስኩና ችግር የለውም ና እቃህን ይዘህ ብዬ እኛ ሙስሊሞች ብቻ ያለንበት ክላስ ቦታ አዘጋጀሁለት።
✍️ሒላል እኛ ክላስ ከመጣ በሗላ ብዙ ወጎችን እያወጋን ተላመድን። አረበኛን በድፍረት እንዳወራ አድርጎኛል ሒላል አላህ ባለበት ይጠብቀውና።
✍️ሒላል 5ወንድ ልጆች አሉት።ከታሰረ ጀምሮ አንድም ቀን ባለቤቱ ልትጠይቀው አለመምጣቷ ገርሞኝ ስጠይቀው ሚስቴ ጠንካራ ናት። እኔጋ ካልሆነ ከቤት አትወጣም አለኝ። ጣፋጭ ነገሮችን ሰርታ ለትልቅ ልጁ ለኻሊድ ትልክልናለች።
✍️የኔ ሚስት አለኝ መንገድ ላይ ስንቀሳቀስ የተራቆተች ሴት ባየች ጊዜ አንገቴን ሰብራ በሒጃቧ ፊቴን ትሸፍነኛለች ብሎኛል 😍
✍️ሒላል 1ወር ከታሰረ በሗላ በዋስትና ተፈቶ ወጣ። ነገር ግን ሒላል እኔን ሐበሻውን ደካማውን የእስርቤት ሷሒቡን የሚረሳ አልነበረም።
✍️ሒላል ከልጆቹ ጋ እየተመላለስ በተለያዩ ሳምንቶች 5 ጊዜ ዘይሮኛል። ይህ ለእኔ ታላቅ ውለታ ነው። ማንም ይህን ያክል የዘየረኝ አልነበረም።
✍️ሒላል ከኢትዮ ሊወጣ በወሰነ ጊዜ 5ልጆቹን ይዞ መጥቶ ዘየረኝና በል ደህና ሁን አላህ ይፈርጅህ ብሎኝ በእንባ ተለያየን። ኻሊድ ፣ዐብደላህ ፣ ዐብደረህማን ፣ኢስላም ፣ዑወይስ ይባላሉ ልጆቹ። አላህ ይጠብቃቸው።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 01:20


የእስርቤቱንም ታሪክ ኢንሻ አላህ

ይለቀቃል እንድታነቡት እና እንዳይበዛባችሁ ተብሎ ነው።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 01:16


📖እውነተኛ ፍቅር😍


🌹ክፍል 1⃣

በቅድመ ኢስላም በጃህሊያ ዘመን ወደ ኢስላም ጥሪ ከመጀመሩ በፊት አስራአምስት አመት ገደማ አንድ ውብና ተክለ ሰውነቱ ያማረ ወጣት ካዕባ አጠገብ ከሚገኘው በኸዲጃ ቢንት ኹወይሊድ (ረዐ) ቤት አጠገብ አለፈ፡፡
ወጣቱ ሲያዩት ፊቱ እንደ በድር ጨረቃ የፈካ ፤ መልከመልካም ፣ የዐይኖቹ ጥቁረት የበረታ ፣ የሽፋሽፍቶቹ ፀጉር ረዥም ፣ ፀጉሩ በጣም የጠቆረ ፣ አንገቱ መለሎ፣ አይኖቹ በተፈጥሮ የተኳሉ ፣ ቅንድቡ ቀጭን እና ረዥም ከሩቅ ሲያዩት እጅግ ሲበዛ ቆንጆ ሲቀርቡት ተወዳጅ ጥርሱ ነጭ አፍንጫው ቀጥ ያለ ነበር፡፡
በወቅቱ የከድጃ ቤትና የዳረል አሰድ ቢን አብድልዑዛ ፣ ቤት ከካዕባው ጥቂት እርምጃ ነበር የሚርቀው፡፡ አንድ የአይሁድ መነኩሴ በከድጃ ቤት ውስጥ ቁጭ ብሎ ሳለ መልከመልካሙን ወጣት አየው ፣ ከድጃንም ወጣቱ ተጠርቶ እንዲመጣ አዘዛት ፣ ወጣቱም በከድጃ አገልጋይ ተጠርቶ መጣ፡፡
አይሁዳዊው መነኩሴ ወጣቱን በትህትና ልብሱን ከትከሻው አካባቢ ገልጦ እንዲያሳየው ጠየቀው ፣ ወጣቱም እንደተጠየቀው አደረገ ፣ አይሁዳዊው ትከሻው አካባቢ ባየው አስደናቂ ነገር ተደሰተ አቅፎም ሳመው፡፡
ሁኔታውን ስትከታተል የነበረችው ከድጃ ለአይሁዱ "ይህንን ድርጊትህን ቁረይሾች ቢያዩህ አንተን ከመቅጣት ትዕግስት የላቸውም " አለች፡፡
በርግጥ የአይሁዱ ድርጊት ለምን እንደሆነ ከድጃን (ረዐ) የገባት ነገር የለም ፣ ወጣቱን ስታየው ፊቱ የፈካና የሚያምር አንደበተ ርቱዕ ነበር፡፡ በሌላ ጊዜ አይሁዱ ለከድጃ እንዲህ አላት፡፡
"በተውራትና በኢንጂል ኪታቦች ላይ ሰፍሮ እንዳየሁት የአንድ ብርቱ ሰው መምጫ እየተቃረበ ነው፡፡ ይህ ሰው የተወለደው እዚሁ በመካ ነው ፣ እናትና አባቱ በልጅነቱ ይሞታሉ ፣ አጎቱ ያሳድጉታል ወደ መዲናም ይሰደዳል ፣ የሻምን ስልጣን በእጁ ያደርጋል ፣ በመካ ያሉትን ጣኦታት በሙሉ ሰባብሮ በማስወገድ ካዕባን ንፁህ ያደርገዋል፡፡"
ከድጃ አይሁዱ የተረከላትን በጥሞና አዳመጠች ፣ በንግግሩም ተማረከች ልቧ ጓጓ ወጣቱንም ለማወቅ ፈለገች፡፡
በሌላ ጊዜ አጎቷ ወረቃን ስለዚው ጉዳይ ጠየቀችው ፤ ወረቃም ወደ ሻምና ሶሪያ በመሄድ የኢንጅልን መፅሀፍ ስላጠናና ስለመረመረ ይመጣል ተብሎ የተተነበየው ታላቅ ሰው ከቁረይሾች እንደሚያገባ በገንዘብ እንደምትረዳውና ከጎኑ እንደምትሆን አረጋገጠላት፡፡
.

የተከበረችው ኸድጃ በዝሆኖች አቆጣጠር ከ15 አመት ቀደም ብላ ከአባቷ ኩወይሊድ ኢብኑ አሰድ አብድልዑዛ ከእናቷ ፋጡማ ቢንቱ ዛኢዳ ተወለደች፡፡ ከድጃ ስሩ ከጠለቀ ጫፉ ከዘለቀ ከተከበረ ነገድና ቤተሰብ የተገኘች ናት፡፡ ከህፃንነቷ ጀምሮ የነገሮችን እውነታ የመከታተልና የማወቅ ጉጉቷ ከዕድሜዋ የላቀ ነበር፡፡ ስለ ንግድ አባቷ ከወንድሞቿ ጋር ሲወያዩ በአትኩሮት ትከታተል ነበር፡፡
ለአቅመ ሄዋን ስትደርስ ብዙ የጋብቻ ጥያቄ ይቀርብላት ጀመር፡፡ እሷ ግን በስሜት ተገፋፍታ ለምርጫ አልቸኮለችም፡፡ ጉዳዩን በጥልቀትና በስፋት በመመርመር ለምትወስደው አቋም ሚዛናዊ መለኪያዎችን መፈለግ ተቀዳሚ ተግባሯ ነበር፡፡ በመጨረሻ ግን አቡሀላህ ኢብኑዚራራህን አገባች፡፡ ከሱም ህንድና ሀላህ የተባሉ ልጆችን አገኘች፡፡ ከድጃ ከአቡሀላህ ጋር ጥቂት አመታት እንደቆየች በሞት ተለያት፡፡ ከዚያ አቲቅ ኢብኑል ኩዘይምን አገባች፡፡ ከሱም አንድ ልጅ ከወለደች በኋላ አቲቅ በሞት ተለያት፡፡ ሀብትና ንብረቱን ወርሳ ተቀመጠች፡፡
ከባሏ ሞት በኋላ የተለያዩ ሰዎች ለጋብቻ ቢጠይቋትም ፍቃደኛ አልሆነችም፡፡ የወንድ አይነት እየተግተለተለ በተለያየ አቀራረብ ደጅ ቢጠናትም ስሜት አልሰጣትም፡፡
አላህ በረቀቀ ጥበብና ማንም በማይደረስበት ሚስጥሩ የማንነት መለኪያ የትልቅነት መገለጫ ሆነው ከቀረቡት ነገሮች ሁሉ እጅግ ብልጫ ያለውን መልካም ነገርን ሁሉ አጠቃሎ የያዘ ሰው አዘጋጅቶላት እንደነበር አስባውም አታውቅም፡፡
ከድጃ ጣኦት አላመለከችም፡፡በጃህሊያ ከጣኦት አምልኮ እንድትቆጠብ ያደረጋት ለአጎቷ ወረቃ ያላት ቀረቤታ ነው፡፡ ወረቃ ኢብኑ ኑፈይል የነሳራዎች መፅሀፍ ከቅድመ አያቶቹ ስለተሰጠው ይህንን መከተል መርጦ ስለነበር ብዙ ዕውቀቶችን ወደተለያዩ አገሮች ሄዶ ተምሮ ብዙ እውቀት ስላገኘ ከድጃ የባዕድ አምልኮ እንዳትከተልና እንድትጠላ አድርጓታል፡፡ የተረጋጋች በሳል ተፈጥሮዋ የሰከነ በመሆኑ ሰዎች "ጧሂራ"(ንፅህት) በሚል በልዩ የማዕረግ ስያሜ ይጠሯታል፡፡ ይህን ስያሜ ከእስልምና በፊት ያገኘችው ነው፡፡
አንድ ወቅት ከቁረይሽ ሴቶች ጋር ሆና በጃህሊያ ጊዜ አመታዊ በዓል በሚያከብሩበት የክብር ቦታ ቁጭ ብላ ሳለ አንድ ሰው ሴቶቹ አጠገብ ሲደርስ "እናንተ የመካ ሴቶች በናንተ ከተማ ነቢይ ሊመጣ ነው ስሙ አህመድ ይባላል፡፡ ከናንተ የቻለ ያግባው " ሲል ይጮሀል፡፡ ሴቶቹና ሌሎች ሰዎች ጭምር በድንጋይ እየደበደቡት አባረሩት፡፡ የተከበረችው ከድጃ ስትቀር
.
.
ይቀጥላል ኢንሻ አላህ🌹

https://t.me/Golden_Speech

ወርቃማ ንግግሮች

20 Dec, 01:16


📖እውነተኛ ፍቅር😍


🌹ክፍል 2⃣

የከድጃ ሀብት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጣ፡፡ በውክልና እሷ ዘንድ በኮሚሽን መቀጠር ከቻሉ ሰዎች መካከል ሙሀመድ (ሰዐወ) አንዱ ነበር፡፡ ወጣቱ ትሁት ሰው አክባሪ የሰውን ገንዘብ ያለ ሀቁ የማይፈልግ ታታሪ ቸር ስራውን ወዳድ በመሆኑ ከድጃ ጋር ከተቀጠረ ጀምሮ ከመካ ከተማ ርቆ በመሄድ እየነገደ ገንዘቧን በእጥፍ አሳደገው፡፡ በዚህም ከድጃ በወጣቱ ኮርታበታለች፡፡ ሙሀመድ ከድጃ ጋር የተቀጠረው እንዲሁ በአጋጣሚ አልነበረም፡፡ የሚያሳድጉት አጎቱ ጥሪት አነስተኛ በመሆኑ እንጂ፡፡
የሙሀመድ አባት አብደላህ ገና ሳይወለዱ ነበር የሞቱት፡፡ እናታቸውን ያጡት ደግሞ በ6 አመታቸው ነበር፡፡ ቢሆንም በአያቱ ዘንድ አደገ፡፡ አያቱ ሲሞቱ አጎቱ ተረከቧቸው፡፡
መሀመድ አጎቱ ጋር መኖር ሲጀምር ፍየል በመጠበቅ ተግባር ተሰማራ፡፡ ግን ብዙም ሳይቆይ አጎትየው የገቢያቸውን መጠን ለማሳደግ ጥረት ማድረግ ጀመሩ፡፡
አንድ ቀን ከድጃ ወንዶችን ወደ ምድረ ሻም በመላክ እንደምታሰማራ ስላወቁ ነጋዴው ወደተባለው ሀገር ለመጓዝ በዝግጅት ላይ ሳሉ ሙሀመድን አስጠርተው ስለሁኔታው ሊነግሯቸው ወሰኑ፡፡
"የወንድሜ ልጅ ሆይ እንደምታውቀው አንዳች የሌለኝ ደሀ ነኝ ፤ ግዜው ደግሞ በድርቅ ተመቷል፡፡ ከድጃ ሰው ቀጥራ እንደምታስነግድ ሰምቻለው በርግጥ የምትከፍለው ገንዘብ አነስተኛ በመሆኑ ደስ አያሰኝም፡፡ እናም ስለዚህ ጉዳይ እሷኑ ባነጋግርልህ " ሲሉ አቡጧሊብ ጥያቄ ለመሀመድ አቀረቡ፡፡ ሙሀመድም እንዲህ አላቸው "አጎቴ ሆይ እንዳሻህ ማድረግ ትችላለህ ሀሳብህ የኔም ሀሳብ ነው መጭው አለም ከዱንያ አለም በላጭ ነው" አሏቸው፡፡
አቡጧሊብ ጊዜ ማጥፋት አልፈለጉም ወንድሞቻቸውን አስከትለው ወደ ኸድጃ ቤት አመሩ፡፡ እሷም ከሀር በተሰራ ባማረ ልብስ ተውባ በፈገግታ ተቀበለቻቸው፡፡
አቡጧሊብም "የተከበርሽው ከድጃ ሆይ እኛ የመጣነው ለጉዳይ ነው ሰዎችን ገንዘብ እየከፈልሽ እንደምታስነግጂ ሰምቻለው፡፡ ለሌሎች በምትከፊይው ላይ ጨምረሽ ተመሳሳይ ስራ እንዲሰራልሽ መሀመድን አትቀጥሪምን? " አሉ
ከድጃም "እንኳንስ ለሚወደድ ለቅርብ ዘመድ ለማይታወቀውም ቢሆን ጥያቄዎ በኔ ዘንድ ተቀባይነት አለው" በማለት አስደሳች መልስ ሰጠች፡፡
አቡጧሊብ አስደሳቹን ዜና ይዘው ወደ መሀመድ (ሰዐወ) ተመለሱ፡፡ ብስራቱን ከነገሩት በኋላ "ይህ ፈጣሪ ላንተ የላከው ሲሳይ ነው " አሉ፡፡
ሩህሩሁ አጎት መጪው ጊዜ ያረገዘውን ቢረዱ ይህ ለከድጃ ከሰማይ የወረደ ፀጋ ነው ባሉ ነበር፡፡ ሆኖም ከዚህ መልካም ዜና በስተጀርባ የሚመጣውን የላቀ ዕጣ የሚያውቅ አንድም ሰው አልነበረም፡፡
እድለኛዋ ከድጃ አቡጧሊብ ያቀረቡትን ጥያቄ በደስታ ተቀበለች ፤ ይህም ሙሀመድ (ሰዐወ) እና ከድጃ (ረዐ) ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቁበት አጋጣሚ ፈጠረ፡፡ ጉዳዩ በመካ ነዋሪዎች ዘንድ ተዳረሰ፡፡ በየአጋጣሚው የታላቁን ሰው መልካም ትሩፋት እውነተኛነት ዘረዘሩላቸው፡፡ ከድጃም ይበልጥ ደስ አላት፡፡ መይሰራ ከተባለው አገልጋይ ጋር ወደ ሻም እንዲሄዱ ለማድረግ መዘጋጀታቸውን አስታወቀች፡፡ ሙሀመድም የተሰጣቸውን አማና ተቀብለው ለንግድ ከመይሰራ ጋር ወደ ሻም አመሩ፡፡


የተከበረችው ከድጃ አንድ ምሽት ተኝታ ህልም አየች፡፡ ከእንቅልፏ እንደነቃችም ስላየችው ህልም ማሰብ ጀመረች በጃህሊያ ጊዜ ህልም ትልቅ ትርጉም ስለሚሰጠው ለህልም ፈቺዎች ለታላላቅ ሰዎች ይነገራቸውና ያስፈቱት ነበር፡፡ ከድጃም የህልሙን ፍቺ ለማወቅ ጓግታ አጎቷ ወረቃ ጋር ሄዳ ህልሟን ነገረችው፡፡

ህልሟም "ፀሀይ ከሰማይ ወየ ምድር ቀጥ ብላ በመውረድ ወደ ከድጃ ቤት በመግባት ቤቷ ውስጥ አበራ፡፡ ቤቱም በብርሀን ተሞላ፡፡ ቤቱም በብርሃን ተሞላ፡፡" ወረቃም ህልሙን በሰማ ጊዜ የጥሩ ጊዜ መምጫ መቃረቡን ተረዳ፡፡ ከዚያም ለከድጃ እንዲህ አላት
"የወንድሜ ልጅ የምስራች ቤትሽ የገባው የነቢይ ኑር ሳይሆን አይቀርም አላህ ሊያከብርሽና ሊያልቅሽ እንደሆነ እጠረጥራለሁ፡፡
ከድጃም "የነቢይ ኑር ምንድነው ?" አለችው፡፡ ወረቃም "የአላህ ብርሀን ነው ወደ ምድር የሚላክ ብርሀን የመጨረሻው ነቢይ መምጫው ተቃርቧል ሰዎችን ከጨለማ ወደ ብርሀን ይጠራል፡፡ ከፀሀይ መውጫ እስከ መግቢያ ያሉ ሰዎች ይከተሉታል፡፡ "
ከድጃ (ረዐ) ወረቃ በነገራት ነገር በጣም ተገረመች፡፡ በሌላ ጊዜ ከድጃ ከቁረይሽ ወይዛዝርት ጋር በካዕባ የክብር ቦታ ቁጭ ብላ ሳለ አንድ አይሁዳዊ "እናንተ የቁረይሽ ወይዛዝርቶች የነቢይ መምጫው ተቃርቧል፡፡ አደራችሁን ለሚመጣው ነቢይ ፍራሽ እንድትሆኑለት የመፅሀፉ ትንቢትም ደርሷል" አላቸው፡፡ ወይዛዝርቱ ግራ በመጋባት አዩት ተሳለቁበትም፡፡ ከድጃ ግን የወረቃ ንግግር ትዝ አላት፡፡
መሀመድ (ሰዐወ) እና መይሰራ ከሻም ተመለሱ፡፡ መይሰራም ስለጉዞው ስላጋጠመው ተአምራት በዝርዝር ለኸድጃ ነገራት፡፡ በጥሩ ትርፍም እንደተመለሱ አወጋት፡፡ ከድጃ ግን ከገንዘቡ ይልቅ የሙሀመድ ሁኔታ ባህሪው ከጉዞው ተአምራት ጋር ተዳምሮ በልቧ እንድትወደውና እንድታፈቅረው አደረጋት፡፡ ስለእሱ ማሰብ ጀመረች፡፡ እንዲህ አይነት ስሜት ከዚህ በፊት ተሰምቷት አያውቅም፡፡ በመደነቅም ለራሷ ጥያቄ ማቅረቧ አልቀረም፡፡ ለመሀመድ (ሰዐወ) የጋብቻ ጥያቄ ለማቅረብ ወሰነች፡፡ ለመሆኑ እርሷ የ40 አመት ወይዘሮ እንደመሆኗ ወጣቱ መሀመድ (ሰዐወ) የጋብቻ ጥያቄዋን ይቀበለው ይሆን? ጥያቄዋ መልስ ባያገኝስ ፤ የሙሀመድን ቤተሰቦች ፊት እንዴት ታያለች?
.
.
.
ይቀጥላል ኢንሻ አላህ🌹

https://t.me/Golden_Speech

ወርቃማ ንግግሮች

19 Dec, 17:27


ህዝቡ በጣኦት ተደበቀ። እርሱ ወደ ሽሽት ሜዳ ጉዞ ጀመረ፤ የሂራእን ዋሻ ክፍት ሁኖ እገኘው፤ በእቅፉም ተሸሸገ። የ አንብብ መልዓክ መጥቶ የዝምታውን ካህንም፦‹‹አንብብ›› አለው። የሰዋዊው ድኩም ልሳንም፦‹‹ማንበብ አይሆንልኝ ›› አለ።

ፍርሃት ስፍራዋን ያዘች፤ የያዘችውንም አንቀጠቀጠች። በአከናንቡኟ እግሩምሯሜ አጉረመረመ፤ የእዝነት ሲሳይም ‹‹አንተ ተከናናቢው! ቁም...›› የሚልን ብስራት ይዞ ተከናናቢን ቀሰቀሰ።

አንቱ የ ‹‹ቁም›› ን ትዕዛዝ የተሸከሙ፣ አንቱ የ ‹‹አስጠንቅቅ›› ን ዘውድ የደፉ፣ አንቱ የዐርሽ እንግዳ፣ የአንቱ የባህታውያኑ የነፍስ ቂብላ፣ አንቱ የነቢያቱ ኢማም...

ህዝቡ በመካነ ልዕልናቸው ተገረመ፣ በምቀኝነት ልሳንም፦‹‹ቁርአን በርሱ ላይ ምነው ባልተወረደ!›› አለ። የመመቀኘት እሳታቸውን አመድ ቢያደርግባቸው ፤ እብድ ነውም አሉ።

አንቱ የውበት ጥቅል፣ አንቱ መላው ምልዐት፣ አንቱ የእርቁ አማላጅ የዘመናት ጌጥ፣ ነቢያት ከዋክብትን መስ'ስለው እርሶ ፀሀይቱን ተኩ። የፈለካቸው መዞርያ ነጥቡም እርሶ ሆኑ፣ በርሶ ዙርያ ከዋክብቱ ሁላ ዟሪ ናቸው።

ለምድር የረፋዷ ፀሀይ፣ የሌሊቱ ጨረቃም ኖት። ፍጥረት በሰው ቢመሰል ነብያቱ በመላ ልብን ወከሉ፤ ሙስጠፋም ሰዐወ ሚስጥራቸው ሆኑ።

የሌሊቱ ጉዞ እንግዳውን ያዘ። የመካን ሀረም ለቆ ከአቅሳው ግቢ ዘለቀ። ባህታውያኑ ነቢያት ከየምኩራቦቻቸው ተሰበሰቡ፤ ከፍጥረተ አለሙ ባህታዊ ኋላ ተሰልፈውም ሰገዱ።

‹‹ሙሳም ዒሳም ዐሰ ቢኖሩ ተከታዮቼ ናቸው፤ ተው እንጂ ዑመር! ›› ከፀሀይ ጋር ጨረቃ ይበጃልን?

ነቢያት የረመዳንን አፅዋማት ቢወክሉ፤ ሙስጠፋ በዒዱ ይመሰላሉ። መላዕክት ተዐምር በመላ ሰማይ ላይ ብቻ እንዳለ ጠረጠሩ፤ የሚዕራጁ ሌሊት በምድሩ ተዐምር ፈዘዙ።

የመላዕክት ከፍ ማለት ጉድ አያስብልም፤ ባለ ክንፍ ናቸው። ጉድ ያሰኘው ፍጥረቱ ስጋ ሁኖ የመውደቅን ባህሪ ለባሹ ከመላዕክቱ በላይ የከነፈ ግዜ ነው።

ጀብራኢል የበረኃው መንገድ መሪ ነበር፤ ከምልክት አልባው የመለኮት በረሀ ዘንድ ሲደርስ እንግዳ ከአስጎብኚው መብለጡን ተረዳ። ‹‹ይኸው አንተም ጌታህም›› ብሎ እጅ ነሳ። እንግዳ ከአውድማው ቅርበት ላይ ወደቀ፤ ከወደ ልቅናው ግርማ፦‹‹የፍጥረት ልሳን ዝም ይበል›› ተባለ።

‹‹አንተ ላይ የውዳሴን ጥግ አልደረስኩ›› አለ የፍጥረት ልሳኑ ጌታን ማላቅ ቢከብደው። የሞገሱ ብርሃን ሊያጠፋው ተቃረበ፤ ‹‹ሰላም ባንተ ላይ›› በሚል የመጥምቅ ውሃ ባይደፋበት...።

ቂያማም ሲቆም ሙሳ አባሉ ነው፣ ዒሳም አጃቢው ነው፣ አደም ነቢን ሰዐወ ሲያይ የሁኔታው ልሳን እንዲህ ይላል፦‹‹የአምሳያ ልጄ፤ የመንፈስ ወላጄ!››

ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም

ወርቃማ ንግግሮች

18 Dec, 12:19


ኢህሳን  ⚪️⚪️⚪️⚪️
🅰️🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤🔤

በቅርቡ የተከፈተ  ሰራተኛና አሰሪ ለሚፈልጉ
😓ሙስሊም  ማህበረሰብ በቀላሉ እንዲገናኙበት
🥳  ታስቦ የተከፈተ አዲስ 🔤🔤🔤 ነው❤️

🥳ቻናሉ ተደራሽ እንዲሆን
😊 ሼር በማድረግ አሰራጩት
🎁
😎በየትኛውም ዘርፍ
😎ሰራተኛ የምትፈልጉ በውስጥ መሥመር
😎አሳውቁኝ ምንም አይነት
😎 ክፍያ ይሁን መስፈርት አይኖረውም
😎 ስለስራው ከመጠየቅ ውጪ

😬@twhidfirst1 🔥

🔤🔤🔤🔤🔤🔤
https://t.me/ihsan_jobs
https://t.me/ihsan_jobs

ወርቃማ ንግግሮች

15 Dec, 02:19


በመታገስና በሶላት ተረዱ…


ወደ አላህ በቀረብን ቁጥር ከሰው መከጀላችንን እናቆማለን በሚደርሱብን ነገሮች ሁሉ መልካም እንደሆኑ እናውቃለን በሶላት ያልቀረበ በችግር ግዜ ያ ረብ ማለት ይከብደዋል።

ትግስትንም ሶላትንም ያዙና አሸናፊ ሁኑ…!!!

~ ሰብሃል ከይር

ወርቃማ ንግግሮች

12 Dec, 14:12


ውዱ መልዕክተኛችን ﷺ በአንድ ሐዲሳቸው ላይ: «የኾነ ጊዜ ይመጣል ከኡመቶቼ መካከል 5 ነገርን የሚወዱ፤ አምስት ነገርን ደግሞ የሚረሱ ሰዎች ይመጣሉ። እነዚህ ሰዎች፦ይህንን ዱንያ ይወዳሉ፤ አኺራን ይረሳሉ። ገንዘብን ይወዳሉ የሒሳቡን ቀን ደግሞ ይዘነጋሉ። ፍጡርን ይወዳሉ ፈጣሪን ይረሳሉ። ሐጢያትን ይወዳሉ ተውበት ማድረግን ይረሳሉ። ቤተመንግስቶችን ይወዳሉ መቃብሮችን ደግሞ ይረሳሉ።» በማለት ተናገሩ።

سيأتي زمان على أمتي يحبون خمسا وينسون خمسا، و يحبون الدنيا و ينسون الآخرة، ويحبون المال وينسون الحساب، ويحبون الخلق وينسون الخالق، ويحبون الذنوب وينسون التوبة، ويحبون القصور وينسون المقبرة

#Category_1: «ዱንያን ይወዳሉ፤ አኺራን ይረሳሉ።»

አላህ «መጨረሻይቱም ዓለም ከመጀመራያይቱ ይልቅ ላንተ በላጭ ናት።» እያለን አይ እኔ ዱንያ ትበጀኛለች ብለን ሳናስተውለው በዚህ ምርጫ ውስጥ የሰጠምን አለን። መጨረሻይቱ ዓለም ሩቅ ይመስለንና የቅርቢትዋን ዓለም አጥብቀን እንይዛለን። የዘላለሙን ዓለም መምረጥ የሚያስከፍለውን መስዋዕትነት ብሎም ህመሙን መክፈል ይከብደንና የጊዜያዊው ዓለም ያስቀመጠልንን አቋራጭ እንመርጣለን። አላህ ከእነዚህ ጎራ ከሚሆኑት አያድርገን

#Category_2: «ገንዘብን ይወዳሉ፤ የሒሳቡን ቀን ይዘነጋሉ።»

ገንዘብ ከሒሳብ ጋር ይተሳሰራል። በተሰማራንበት ዘርፍ ላይ ቀን በቀን ወጪ እና ገቢያችንን እንተሳሰባለን፤ በፍቅሩም እንሰክራለን። ጌታችን ሱረቱል ፈጅር ላይ «ወቱሂቡነል ማለ ሁበን ጀማ: ገንዘብንም ብዙ መውደድ ትወዳላችሁ።» እንደሚለን እጅጉኑ ገንዘብ ያውረናል። ገንዘቡን በሐላል መንገድ ያላገኘነው እንደሆነ ብሎም አላህ ፊት የምንቆምበትን የሒሳብ ቀን የማንፈራ እንደሆነ የሰው ሐቅ መውሰድ ላይ ፤ ስራ አሰርቶ አለመክፈል ላይ፤ ማጭበርበር እና ሚዛን ማጓደል ላይ ብርቱ እንሆናለን። ጌታችን ፊት የምንቀርብበት ጊዜ ሩቅ ይሆንብናል፤ ከዘንጊዎቹም እንሆናለን። የምንገነዘበው የውመል አኺር ስንሄድ ነው። የምንገዘብበትን moment ጌታችን በዚህ መልክ ይገልፀዋል

وَجِيءَ يَوْمَئِذٍ بِجَهَنَّمَ ۚ يَوْمَئِذٍ يَتَذَكَّرُ الْإِنسَانُ وَأَنَّىٰ لَهُ الذِّكْرَىٰ

«ገሐነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?» ... አላህ ከዚህ ጎራ ከመሆን ይጠብቀን!

#Category_3: «ፍጡርን ይወዳሉ፤ ፈጣሪን ይረሳሉ።»

የሰዎችን attention፤ የሰዎችን ውዴታ crave በሚያደርጉት ልክ የፈጣሪያቸውን ውዴታ ለማግኘት አይቻኮሉም። አንድ ወንድ ወይም ሴት ለሚወዳት/ ለምትወደው ሰው ሲሉ እራሳቸውን አሳልፈው እንደሚሰጡት ሁሉ ለፈጠራቸው አምላክ ብዙ መስዋዕትነት የማይጠይቀውን አምልኮ ተግባር ላይ ለማዋል ይሰስታሉ። ቪው ለማግኘትና ፎሎወር ለማብዛት መከራ በሚበላበት ተጨባጭ የአል ወዱድ'ን እይታ እንዘነጋለን። ጌታችን ሲወደን መላዕኮችን ሁሉ "እገሌን ውደደው" ብሎ የማይተመኑ ፎሎወሮችን እንደሚሰጠን እንዘነጋለን።

አላህ ያስረዳን!

#Category_4: «ሐጢዓትን ይወዳሉ፤ ተውበት ማድረግን ይረሳሉ።»

ሰዎች ሐጢዓትን እንወዳለን ብለው ላይናገሩ ይችላሉ፤ ነገር ግን ሐጢዓት'ን የመስራት መንገድ ቀላል ሆኖብን የተውበት መንገድ ሲከብደን ማዕሲያ'ን እንላመዳለን። "ምን ችግር አለው?" ወደሚል ድፍረት'ም ያደርሳል። አላህን ሐያዕ ማድረግ ይቀራል። proudly መጥፎ ስራዎችን publicly ማሳየትን Normalize እናደርጋለን። አንዳንዶች ደግሞ ዝሙትን እንደፈለጉ exercise ለማድረግ የእስልምና ህግጋቶች'ን ሽፋን ማድረግ ላይ ብልጥ ለመሆን ይሞክራሉ። ሐጢዓት ላይ መለከፍ፤ የተውበትን መንገድ መርሳት ማለት ይሄ ነው። 😢... አላህ ከዚህም ጎራ ከመመደብ ይጠብቀን!

#Category_5: «ቤተመንግስቶችን ይወዳሉ፤ መቃብሮችን ደግሞ ይረሳሉ።»

Fancy የሆኑ፤ የተንጣለሉ ንብረቶችን እንደምንመኘው ሁሉ መቃብር ስፍራዎችን መጎብኘት ሩቅ ይሆንብናል። የታመመ መጠየቅን በጊዜ ሂደት እንረሳለን። ቁስ ሟሟላት ላይ በተለይም ውድ የሆኑ ንብረቶችን own ማድረግ እንደምንወደው ሁሉ ከዚህ ከልክ ያለ ፍቅርን የሚያስታግስልንን ሞት እጅጉኑ እንዘነጋለን። "እገሌ ሞተ" የሚል ዜና ብዙም አያስደነግጠንም። ይልቁኑ በብዛት መፎካከር ላይ እናተኩራለን፤ አላህ እራሱ ሱረቱል ተካሱር ላይ: «በብዛት መፎካከር ጌታችሁን ከመገዛት አዘናጋችሁ» ካለ በኃላ "ሐታ ዙርቱሙል መቃቢር: መቃብሮችን እስከ ጎበኛችሁ ድረስ።" የሚለውን ያስከትላል።

እገሌ የሆነ ብራንድ ልብስ ለበሰ እኛም እንደ እገሌ ወይም ከሱ የተሻለውን ለመልበስ እንሽቀዳደማለን። እገሊት የሆነ ፀዴ ቤት ገዛች እኛም እሷን ለመምሰል ወይም በልጦ ለመገኘት የፉክክር ሜዳ ውስጥ እንዘፈቃለን። we can talk about smart phones, brand bags , car and others.... መሐል ላይ ግን ሁሉን ያስገኘውን አምላክ ማመስገን ይረሳል። የሰጠውን በሰከንድ ልዩነቶች ውስጥ መውሰድና ማውደም የሚችለውን ጌታ ይዘነጋል። ሐብቱ delusion ውስጥ ከቶን አላህን ከመገዛት ያዘናጋናል።

ሰሐቢዩ ዑበይ ኢቢን ካዕብ ረዲየሏሁ አንህ የአላህ መልዕክተኛ ﷺ የቁርኣን አያህ እስኪመስለን ድረስ በብዙ አጋጣሚ ላይ እንዲህ ይሉን ነበር ይላሉ።

لو أن لابن آدم وادياً من ذهب أحب أن يكون له واديان

«የአደም ልጅ የወርቅ ሸለቆ ቢኖረው እንኳን፤ የተሰጠውን አይነት ሌላ ይመኛል።» አሉን፤ ይህ ንግግራቸው'ም ሱረቱል ተካሱር ከወረደ በኃላ ገባን ይላሉ ዑበይ። 🤎

ፉክክሩ ደግሞ ቀብር እስክንገባ የሚከተለን ነው። ምክንያቱም እነዛ ዘመናችንን የተፎካከርንባቸው ሐብቶች፤ ከጌታችን ያዘናጋን ንብረት ስንሞት ዋጋ አይኖረውም። መቃብር ይዘነው የምንገባው ስራችንን እና ስራችንን ብቻ ይሆናል። አላህ ከእነዚህ ምድቦች ውስጥ እንዳንሆን ይጠብቀን! አሚይንን
Nadia Biya
@highlight

ወርቃማ ንግግሮች

12 Dec, 09:17


ኢማም አውእዘኢ አንድ ጥበበኛ አንድን ታሪክ እንዲህ ነገሩኝ አሉ ።

የሆነ ጊዜ ጂሀድ መሄድ ፈለኩና መንገዴ ጀምሬ እየሄድኩ ሳለ ምሽት ላይ ዱኳን አገኘሁና ጠጋ አልኩኝ
እጅና እግሩ የተቆረጡ : አይኖቹ የጠፉበት አንድ ሰው ተመለከትኩ ሰውየው "አላህ በኔ ላይ የዋልክልኝ ውለታ ለማንስ ውለሀል
በርካታ ምስጋናወችን አመሰግናለሁ አልሀምዱሊላህ እያለ ይደጋግም ነበር ።

እኔም ኢማኑን ለመፈተሽ የትግስቱን እውነተኝነት ለማወቅ ፈለኩና እንዲህ ሲል ጠየኩት ... ?

ስለየትኛው ፀጋ ነው የምታወራው ምን እንዳደረገህ አልተመለከትክም ወይ አልኩት?

ሰውየውም:- እሱን የሚያስታውስ ምላስ ሰቶኛል: በፈተናወች ላይ መቋቋም የሚችል አካል ሰቶኛል ከሰማይ ላይ እሳት አዝንቦብኝ ቢያቃጥለኝ ለራሱ
ውዴታየ ቢጨምር እንጂ ምንም አይቀንስም አለኝ ።

እኔን አንድ ጉዳይ አለኝ ተባበረኝ አለኝ ?
እኔም :-ችግር የለውም ደስ ይለኛል አልኩት
አንድ ልጅ ነበረኝ ለሶላት ኡዱ ሳደርግ ላፈጥር ስል
የሚያግዘኝ ከትናንት ጀምሮ አጥቼዋለሁ ፈልግልኝ ስለሱ መረጃ አምጣልኝ አለኝ ?

እኔም ልጁን ፉለጋ ወጣሁና ትንሽ እንደተጎዝኩ
አውሬ ገሎት እየበላው ተመለከትኩ ።

እኔም ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን አልኩኝና
እንዴት ነው የምነግረው ስል አሰብኩ ?..

አላህ በውስጤ አፅናናውና መረጃውን ንገረው
የሚል ሀሳብ አመጣልኝ ....
ወደ ሰውየውም ተመልስኩና ሰላምታ አቅርቤለት መለሰልኝ ...

እኔም:- አንድ ነገር ብጠይቅህ ትመልስልኛለህ ወይ ስል ጠየኩት ?
እሱም:- በምጠይቀኝ ነገር ላይ እውቀት ካለኝ እነግርሀለሁ አለኝ!

ከነብዩላህ አዩብ አለይሂ ሰላም እና ካንተ አላህ ዘንድ
የተከበረ ማነው ስል ጠየኩት?
እሱም አዩብ ናቸው አ ከኔ የተሻሉም ደረጃቸውም ከፍ ያለ ነው ሲል መለሰልኝ

እኔም :- አዩብን አላህ አይደል ፈትኖቸው ትግስት ያደረጉት
የቀረቦቸው ወዳጆቻቸው ሳይቀር እንዲርቁ የሆኑት....
እሱም:- አዎ አለ
እኔም :-ልጅህን አውሬ በልቶታል
እሱም:- አልሀምዱሊላህ አላህ በልቤ ላይ በዱንያ ምንም ቁጭት አላደረገብኝ ብሎ እስትንፍሱ ተቆረጠና ሞተ ።

እኔም የሚያስተጣጥበኝና የሚያቀባብረኝ ሰው መፈለግ ጀመርኩ ከዛም ልክ እንደኔ ለጂሀድ የወጡ ሰወችን አገኘሁና ነገሩን ነገርኮቸው ዱዓ አድርገውለት አጥበን ከፍነን ቀበርነው ።

የዛች ቀን ለሊት ታዲያ በህልሜ ይህን ሰው
የጀነት ልብስ (ኹድር) ለብሶ ተመለከትኩት ባልደረባየ ነሃ አልኩት በመገረም ?
እሱም :-አዎ አለኝ
እኔም:- ይህንን ደረጃ በምን አገኘሀው አልኩት?
እሱም :-ይህ ደረጃ በፈተና ላይ የታገሱ ትግስተኞች
በምቾት ጊዜ አላህ የሚያመሰግኑ ደረጃቸው ነው አለኝ ።

ኢማም አውዘኢም ከዛች ቀን ጀምሮ ጥበበኛው ይህንን ከነገሩኝ ብኋላ የሚፈተኑ ሰወችን መውደድ ጀመርኩ ።

ይህ ታሪክ ኢብኑ ከሲር "ታሪኹ ዲመሽቅ የሚለው መፅሀፍቸው ላይ እንዲሁም ዘሀቢ ተስኪረቱ አልሁፍዝ የሚለው መፅሀፍቸው ላይ አስቀምጠውታል ።

አላህ ዘንድ በላጭ የሚወደድ ተግባር አላህ በሰጠን ነገር ላይ መጥፎም ይሁን ኸይር ነገር መውደድ ነው ።

የሰው ልጅ ምንም ቢፈተን ባሪያ መሆኑን መርሳት የለበትም ። አላህ ምንም ያህል ቢፈትን ጌታ መሆኑ መታወቅ አለበት ።
ባሪያ ደሞ በሀለቃው ውዴታ ስር ነው ። አላህ ዘንድ የደረሱት ልባቸው ላይ እንደነዚህ አይነት ኢማን ያላቸው ናቸው ።

ወርቃማ ንግግሮች

09 Dec, 06:42


በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።

የአላህ ባሪያ መሆን እንዴት ይጥማል! እንዴት ደስ ይላል አስቡት ወላህ!

እንደ ሰው ያሰብከው ሲሳካልህም ሆነ ስትደናቀፍ የምንጊዜም መጠጊያህና መሸሻህ አላህ ብቻ ነው።ይሄንን የማያውቅና ዕድሜ ልኩን የርሱ ጉዳይ በእጁ የሆነውን የአላህን ስም አንድ ጊዜ እንኳን «ያ አላህ!» ብሎ ሳይጠራ ዱንያን የሚሰናበተውን እድለ-ቢስ ብዛት አስተውል!።መዓዘሏህ!።

አላህ ነው የነገሮችህ ሁሉ ቁልፍ በእጁ ያለው፣የፈጠረህ፣ሙስሊም ያደረገህ፣በአንተ ላይ ፀጋዎቹ መች ተዘርዝረው ያልቁና።አስተውላቸው፣አመስግነውም።

ሰዎችማ ስኬት ላይ ሆነህ ካዩህ፣ወዳንተ ለመጠጋት ወደ ራሳቸውም ሊያስጠጉህ ብዙ ይጥራሉ።«እርሱ እኮ ዘመዴ ነው፣ጓደኛዬ ነው፣ወዳጄ ነው...ወዘተ» ይሞግታሉ።ለምሳሌ በዱንያ ጉዳዩ ከፍ ያለ የሚመስለን ሀብታምና ባለ-ስልጣን ሆኖ የሁሉም ዘመድ ያልሆነ ማን ኣለ?።

ስትደናቀፍ፣ስትከስር፣በሙከራህ ላይ ስትወድቅ፣ከስልጣንህ ስትባረር...ወዘተ ከአንተ ጋር ዝቅ የሚሉት የቅርብ ቤተ-ሰቦችህና ትክክለኛ ወዳጆችህ ብቻ ናቸው።

አምላክህ አላህ ግን በከፍታህ ጊዜም ሆነ በዝቅታህ ጊዜ ለርሱ ሂክማ(ያንን የፈለገበት ጥበብ) ኣለው።ሁሌም በአንተ ጉዳይ ላይ የርሱ ውሳኔ ነው የሚፈፀመውና አብዝተህ ተጠጋው፣ውደደው፣ተማፀነው፣መቼም ቢሆን ጥሎ አይጥልህምና።ቆንጠጥ ካደረገህም ዱንያ ኣኺራህ እንዲሳካ፣ረስተሀው ከነበረም ታስታውሰው ዘንድ፣በጀነት በስራህ የማትደርሰውን ከፍታ ያጎናፅፍህ ዘንድ...ወዘተ ሂክማዎች ኣሉት ረቡና።

ይሄኔ ነው የርሱ ባሪያ የመሆንን ጣዕም የምታጣጥመው።ይሄንን አይነቱን አማኝ አስመልክተው ነቢዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሙስሊም በዘገቡት ሀዲስ የሚከተለውን ብለዋል፦ «የሙዕሚን ጉዳይ ምንኛ ያስደስታል ያስደንቃል፣መልካምን ነገር ካገኘ አላህን ያመሰግንና ለርሱ ኸይር ይሆንለታል፣መጥፎ ነገር ከነካውም ይታገስና ኸይር ይሆንለታል።ይሄ ለሙዕሚን እንጂ ለሌላ ሰው የማይገኝ እድል ነው።»

ታድያ የዝህ ሩሕሩህና እጅግ መልካም፣በመውደቅም ሆነ በመነሳት፣በማግኘትም ሆነ በማጣት ውስጥ ደረጃህን ከፍ የሚያደርግልህ አምላክ የአላህ ባሪያ መሆን በጣም አያስደስትምን?።

ዛሬ በዙሪያህ ያሉ፣ቤተ-ሰብ፣ወዳጅ፣ዘመድ ሌሎችም በሞት ይለዩሃል።እድለኞች ከሆንን በጀነት መገናኘት ቢኖርም።አላህ ግን ዱንያም ሆነህ፣በርዘኽ(ጣረሞት ይዞህ ሞተህ ከተቀበርክበት ለሂሳብ እስከምትቀሰቀስበት) ባለውም፣ተቀስቅሰህ በአርደልመሕሸር፣በአረሷቱ የውሚልቂያመህ፣ተሳክቶ ጀነቱን አስወርሶህም፣አያድርገውና በሌላም ሁኔታ ሆነህ ለዘልዓለም ከርሱ የማትብቃቃ፣ሁሌም የሚያስፈልግህ፣ሁሌም ጉዳይህን ፈፃሚ፣ውለታውን ከምንም ልታነፃፅረው የማትችል...በቃ በጥቅሉ አስገኚህና አምላክህ እርሱ ነው።
አልሐምዱሊላህ ዓላ ኒዕመቲልኢስላም!

ያረብ ሙስሊም አድርገህ እንጂ ኣኺራ አትውሰደን።

አቡ አብዲላህ
አልመዲነቱልሙነወረህ
ጁማደልዑላ 1446 ዓ.ሂ።

ወርቃማ ንግግሮች

09 Dec, 06:41


ግብህን ካላወክ የትኛውም መንገድ ይወስድሃል

“ቁም ነገሩ ከየት እንደመጣህ አይደለም፣ ዋናው ቁም ነገር ወደ የት እንደምትሄድ ማወቅህ ነው” – Brian Tracy

አንድ መንገደኛ ሰው ረጅምና አድካሚ የሆነ ጎዳናን ካለፈ በኋላ መንትያ መንገዶች ላይ ደረሰ፡፡ በዚያ የቆመን አንድ ሌላ የሀሃገሩን ሰው አየና፣ “ከእነዚህ ሁለት መንገዶች ትክክለኛው መንገድ የቱ ነው?” ብሎ ጠየቀው፡፡ ይህ የሃገሩ ሰው፣ “መሄድ የምትፈልገው ወደ የት ነው?” ብሎ ለመንገደኛው ጥያቄውን በጥያቄ መለሰለት፡፡ መንገደኛውም፣ “ወደ የት መሄድ እንደፈለኩ ገና አላወኩም” አለው፡፡ የቆመውም ሰው፣ “እንግዲያውስ፣ ሁለቱም ትክክለኛ መንገዶች ናቸው” በማለት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መለሰለት፡፡ መንገደኛው፣ “የምትሄድበትን ካላወቅህ የትኛውም መንገድ ይወስድሃል” የሚልን መልእክት ተቀብሎ፣ “መልእክቱ ገብቶኛል” በሚል ዝምታ ተዋጠ፡፡

ብዙ ሰዎች በደመ-ነፍስ ነው የሚኖሩት፡፡ ከየት ተነስተው ወደ የት መሄድ እንዳለባቸው በቅጡ አያውቁትም፡፡ ወደ የት እንደሚሄዱ ማወቅ በሕይወት ላይ ያለውን ተጽእኖ በፍጹም አስበውት አያውቁም፡፡

የግብ ጉዞ የምርጫ ጉዞ ነው - “የትኛውን ጎዳና ብመርጥ ወደ ዋናው የሕይወቴ አላማና ራእይ ያደርሰኛል” የሚል ምርጫ! ግቡን በቅጡ ያላወቀ ሰው የመጣውን ያስተናግዳል፣ ወደተከፈተለት ይገባል፣ ጊዜአዊ ደስታን በሰጠው ነገር ላይ ጊዜውን ያባክናል፡፡

ሕይወት በምርጫ የተሞላች ነች፡፡ ጠዋት በስንት ሰአት ከመኝታዬ መነሳት እንዳለብኝ ከምወስነው ውሳኔ አንስቶ ማታ በስንት ሰአት ወደመኝታዬ መሄድ አለብኝ እስከሚለው ድረስ የምንመርጠው ምርጫና የምንወስነው ውሳኔ በአላማችን ላይ ጣልቃ ይገባል፡፡

“ብዙ ሰዎች የሚያስፈልጋቸው አሳ እንዳልሆነ ሳይገባቸው እድሜ ልካቸውን አሳ ሲያጠምዱ ይኖራሉ” –Henry David Thoreau

“የምትፈልገውን ነገር ካልተከታተልከው አትጨብጠውም፡፡ ካልጠየክ መልሱ ሁልጊዜ የእምቢታ ነው፡፡ ወደፊት ካልተራመድክ ዘወትር ራስህን ባለህበት ታገኘዋለህ” – Nora Roberts

“ግቡ አልደረስ ያለ ሲመስልህ መቀየር ያለብህ ግቡን አይደለም አካሄድህን እንጂ” - Unknown Source


🍂🙏

ወርቃማ ንግግሮች

06 Dec, 18:11


📣  🎈ተጀመረ ⭐️🔈
​•┈┈•┈┈•⊰✿◇✿⊱•┈┈•┈┈•

ርዕስ :- ስለ ኢማሙ አህመድ ታሪክ🎤

📚 ኡስታዝ አቡ ሙዓዝ ሀሰን⭐️
      ተ
⭐️
             ጀ
⭐️
                  መ
⭐️
                          ረ
⭐️
ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም!

ሊንኩን ለሌሎችም ሼር አድርጉት

 ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘ ➘ ➘  ➘ ➘ ➘➘ ➘
https://t.me/tdarna_islam?livestream
https://t.me/tdarna_islam?livestream

ወርቃማ ንግግሮች

06 Dec, 06:59


⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️📡

አዲስ የሙሀደራ ፕሮግራም

በትዳር እና ኢስላም ቻናል

ተጋባዥ ኡስታዞች
⭐️
➡️አብዱ ሸኩር አቡ ፈውዛን
➡️ዶክተር ሰኢድ ሙሳ
➡️አቡ ዑበይዳህ

ርዕስ በሰአቱ ይገለፃል ➷

ቀን እና ሰዓት ዛሬ ጁማዐ
ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ➡️

የሚተላለፍበት ቻናል
⭐️ t.me/tdarna_islam
t.me/tdarna_islam ⭐️

ወርቃማ ንግግሮች

05 Dec, 08:12


🎁 ihsan jobs
ኢህሳን
ይህ ቻናል ለሙስሊሙ ማህበረሰብ
ይጠቅም ዘንድ ታስቦ የተከፈተ የስራ ማስታወቂያ
የምንለቅበት አዲስ ቻናል ነው 💎

በቻናሉ ነፃ ማስታወቂያ እንለቃለን
ከናንተ የሚጠበቀው የትኛውም
ማስታወቂያ በውስጥ መሥመር
ለኛ ማሳወቅ ብቻ ነው ➡️

እኛም በነፃ ከሸሪዓ የማይጋጩ ስራዎች
አጣርተን በቻናሉ እንለቃለን
⭐️ @twhidfirst1
🌟 @Tolehaaaaaa
🌟 @AbuNuhibnufedlu

https://t.me/ihsan_jobs
https://t.me/ihsan_jobs

ወርቃማ ንግግሮች

30 Nov, 04:46


⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️📡

⭐️የመተዋወሻ እና ለህፃን አቲካ
⭐️የትብብር  ፕሮግራም

በትዳር እና ኢስላም ቻናል

ኑ! በልብ ህመም እየተሰቃየች የምትገኘው ህፃን አቲካን ሰበብ እንሁናት

በእለቱም ተጋባዥ ኡስታዞች እና ወንድሞች:
⭐️
➡️ኡስታዝ አቡ ሂበተላህ🎤
➡️ኡስታዝ ዓብዱረዛቅ ባጂ 🎤
➡️ኡስታዝ ኢብራሂም ኸይረዲን 🎤
➡️ኡስታዝ አቡ ዑበይዳህ🎤
➡️አቡ ሁዘይፋህ (ሰዒድ)🎤
➡️አቡ ማሂ (ሙሐመድ ኢድሪስ)🎤

የህፃን አቲካ ህመም ምንድነው?👇
t.me/tdarna_islam/4859?single
t.me/tdarna_islam/4863
⬆️
ቀን እና ሰዓት ነገ እሁድ 22/03/2017
ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ➡️

የሚተላለፍበት ቻናል
⭐️ t.me/tdarna_islam
      t.me/tdarna_islam ⭐️

ወርቃማ ንግግሮች

30 Nov, 04:44


ሙስሊማት ያልሆኑ ሴቶችን ማግባት
~
ለሙስሊም ወንዶች ከነ ጭራሹ ሃይማኖት የሌላቸውን ሴቶች ማግባት ፈፅሞ አይፈቀድላቸውም። ሙስሊማት ያልሆኑ ሴቶችን ባጠቃላይ ማግባትም እንዲሁ የተፈቀደ አይደለም። ከዚህ ተለይቶ የሚወጣው ራሳቸውን ከዝሙት የሚጠብቁ ክርስቲያን ወይም አይሁድ ሴቶችን (ኪታቢያት) ማግባት ብቻ ነው። ክርስቲያን ወይም አይሁድ ሴቶችን (ኪታቢያት) ማግባት እንደሚፈቀድ ግን ቁርኣን ውስጥ ተጠቅሷል። አላህ እንዲህ ይላል፡-
(وَالْمُحْصَنَاتُ مِنَ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ مِنْ قَبْلِكُمْ)
“ከነዚያ ከናንተ በፊት መፅሐፍ ከተሰጡት (አይሁድና ክርስቲያን) ሴቶች ጥብቆቹም (ልታገቧቸው የተፈቀዱ ናቸው።)” [አልማኢዳህ፡ 5]
.
ይህንን መነሻ በማድረግ ሙስሊም ካልሆኑ ሴቶች ጋር ጋብቻ የሚመሰርቱ ሙስሊም ወንዶች አሉ። ነገር ግን እዚህ ላይ የቁርኣኑን መልእክት በደንብ ማጤን ያስፈልጋል። ጋብቻ የተፈቀደው በመልካም ስነ ምግባር ከሚታወቁ ራሳቸውን ከዝሙት ከጠበቁ ሴቶች ጋር ነው። ይሄ ሁኔታ ባልተሟላበት ዝም ብሎ ልብ ስላዘነበለ ብቻ ወይም ፍቅር ላይ ስለወደቁ ብቻ የሚፈፀም ልቅቅ ያለ ህግ አይደለም። ስለዚህ የቁርኣኑን መልእክት ለስሜታዊ ዝንባሌያችን ምርኩዝ እንዳናደርግ መጠንቀቅ ይገባል።
.
በዚህ ዘመን ሙስሊም ያልሆኑ ህዝቦች ከጋብቻ በፊት ያለ ህይወታቸው እጅግ የተጨመላለቀ እንደሆነ በተጨባጭ እያየን ነው። ዝሙቱ ቀርቶ ከትዳር ውጭ መውለዱ እንኳ እንደ ‘ኖርማል’ እየተቆጠረ ነው። ሰፊ እውቅና ያላቸው ሰዎች ሳይቀሩ ህዝብ በሚከታተለው ሚዲያ ላይ ቀርበው “ትዳር የለኝም፣ ግን ልጅ አለኝ” ሲሉ ምንም አይሰቀጥጣቸውም። ልጅ እንዳላቸው የሚታወቁ ግን ትዳር ባለመመስረታቸው የተነሳ ዛሬም “ወይዘሪት እንትና” እየተባሉ የሚጠሩ ብዙ ናቸው። ባጭሩ ከትዳር በፊት የዝሙት ህይወት ማሳለፍ ብዙዎቹ ዘንድ ነውርነቱ ቀርቷል። እንዲያውም “ዝሙት” መባሉ ቀርቶ “ከጋብቻ በፊት ግንኙነት” እየተባለ ነው እየቀረበ ያለው። ይሄ ከጋብቻ በፊት ያለ ግንኙነት ምናልባት በስሱ ከተነቀፈም በፀያፍነቱ እየተኮነነ ሳይሆን ለቀጣይ ህይወት መሰናክል እንዳይሆን ያክል ብቻ ተራ የግል አስተያየት ሆኖ ነው የሚቀርበው። በዝሙትነቱ ሳይሆን ለሴቷ ከሚያስከትለው ጥቅምና ጉዳት አንፃር ብቻ ነው የሚቃኘው። ዝሙት፣ ማመንዘር ይህን ያክል ቀሏል። እንዲያውም ብልግና እንደ አራድነት፣ ጨዋነት ደግሞ እንደ ፋራነት እየተቆጠረ ነው።
ቁርኣናችን ደግሞ ከመፅሐፉ ሴቶች ጋር ጋብቻን የፈቀደው “ከዝሙት የተጠበቁ መሆናቸው” ከታወቁት ጋር ብቻ ነው። ይሄ መስፈርት ባልተሟላበት ከነሱ ጋር ትዳር መፈፀም አይፈቀድም። ይሄ አንድ ነው።

ሁለተኛ:- ልጆችህን በኢስላማዊ ስርአት የምታሳድግበት ሁኔታ መኖር አለበት። አንዲት ሙስሊማ ያልሆነች ሴት ከዝሙት የተጠበቀችና ግብረ ገብ ብትሆን እንኳ በዚህ ዘመን ልጆችህን እርሷ በምትፈልገው እምነትና መንገድ ላይ ማሳደግ ብትሻ የሚያግዳት ገደብ የለም። በዚህ የተነሳ ልጆች እምነታቸው ሊቀየር ይችላል። ይሄ በተጨባጭ እየገጠመ ያለ ዘግናኝ ጥፋት ነው። ሙስሊማት ካልሆኑ ሴቶች ጋር ትዳር ፈፅመው ከዚያ ልጆቻቸው የከ'ፈ'ሩ ስንቶች ናቸው? አንዳንዶቹ እንደዋዛ ልጆቹ 18 አመት ሲሞላቸው ሃይማኖታቸውን ይመርጣሉ ይላሉ። ይሄን ሁሉ አመት ኢስላምን አልተማረም፣ ሶላት የለም፣... ። በዚያ ላይ ለልጆች ከአባቶች ይልቅ እናቶች የበለጠ የቀረቡ ናቸው። ጊዜው አይነቱ የበዛ የሞራል ዝቅጠት የተንሰራፋበት ነው። ከስነ ምግባር ለተኳረፈ ትውልድ ከኢስላም ይልቅ ሌሎች እምነቶች ሊቀርቡት ይችላል። በነዚህና መሰል ምክንያቶች የተነሳ ልጆቹ ኢስላምን የመያዛቸው እድል የመነመነ ይሆናል። እንዲህ አይነት ከባቢ ባለበት ደግሞ ሙስሊማት ያልሆኑ ሴቶችን ማግባት አይፈቀድም።

ሶስተኛ፦ ከላይ ከተጠቀሱት ነጥቦችም ባሻገር በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት ተግባር የሚፈፅሙ አካላት የራሳቸውም እምነት ጭምር አደጋ ላይ የመውደቅ እድሉ ሰፊ ነው። ወንድ ተከትለው የሚከ - ፍሩ እንዳሉ ሁሉ ሴት ተከተለው የተበላሹ ብዙ ናቸው። ይሄ የከፋው አደጋ ነው።
.
ስለዚህ እነዚህ መስፈርቶች ባልተሟሉበት እና ስጋት በተደቀነበት ሁኔታ ከመፅሐፉ ሴቶች ጋር ጋብቻ መፈፀም የሚፈቀድ አይደለም። ታላቁ የዘመናችን የሐዲሥ ሊቅ ሸይኽ ሙሐመድ ናሲሩዲን አልአባኒይ ረሒመሁላህ ቀደም ብለው የተጠቀሱትን ሁለት ቅድመ ሁኔታዎች በመጥቀስ በዚህ ዘመን ከክርስቲያን ሴቶች ጋር ጋብቻ መፈፀም እንደማይቻል አጥብቀው ያሳስባሉ። [ሲልሲለቱል ሁዳ ወኑር ቁ. 523]

እንዲያውም ኢስላም ከሙስሊማት ውስጥ እንኳ አላህን መፍራትና ግብረ ገብነት ያላቸውን ሴቶች እንዲያገቡ ነው ወንዶችን የሚያነሳሳው። ይህንን ህግ መጠበቅ ለራስም፣ ለቤተሰብም፣ ለሚወለዱ ልጆችም፣ ለሙስሊሙ ማህበረሰብም፣ ለኢስላምም ውለታ መዋል ነውና ተገቢውን ትኩረት ልንሰጠው ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል:-
https://t.me/IbnuMunewor

ወርቃማ ንግግሮች

29 Nov, 05:29


ሙስሊም ካልሆነ ወንድ ጋር አጉል ቅርርብ ውስጥ የገባችሁ እህቶች በጊዜ ከሰመመናችሁ ውጡ። በፍቅር ምርቃና እንደ ዋዛ ያቆራረጡት አደገኛ መንገድ መመለስ ሲያስቡ ዳገቱ ልብን ሊፈትን ይችላል። ውሃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው። መጨረሻችሁ ኩ- ፍ- ር ከመሆኑ በፊት በጊዜ ንቁ። ርቀቱ ሲጨምር መመለሻው ይከብዳል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor

ወርቃማ ንግግሮች

28 Nov, 18:32


☔️ወደ ቀሶሳችን☔️

✍️እስርቤት ማለት
👉ሒወት ውስጥ ያለ ሒወት
👉ከተማ ውስጥ ያለ ከተማ
👉ሌላ ዐለም የማይመሳሰለው ዓለም ነው ይሉታል የቃላት ሊቆች።

✍️በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ዒደልፊጥርን እያከበርን እንገኛለን። ዱርዬው መለኛ ነውና በተለያዩ ሚስጥራዊ መንገዶች ሞባይል እና የተለያዩ ነገሮችን ያስገባሉ። እቃውም መጥቶ ሲራገፍ 😂መርከበኛው እቃ አራግፏል ይላሉ። መርከበኛ ይሉታል በራሳቸው መንገድ መስመር ዘርግተው እቃውን ስንት የፍተሻ ኬላን አልፎ የሚያደርስላቸውን። እኛም ዒዱን በማስመልከት የሐፈዝናቸው ወዳጅ ዘመድ ቁጥሮች ጋ እየደወልን ዒዱኩም ሙባረክ እንላለን እንዳንዱ ተፈታህ እንዴ አንዳንዱ ደግሞ ስልክ ከየትህ ነው በሚል ጥያቄ ያደክሙናል። በዚህ መልኩ የቤተሰብን ድምፅ ስንሰማ ውጭ ላይ ያለውን የዒድ ድባብ ስናስታውስ ቁዘማም ደስታም ይደበላለቅብናል።
✍️ጊዜው የኮሮና ወረርሽኝ አገሪቷን በፍርሓት የሸበበት ጊዜ ነበር።ነገር ግን እስረኛው የ7ሰዓት ዜናን በጉጉት ይጠባበቃል ለምን መሰላችሁ በኮሮና የተያዙ ሰዎች ቁጥር ጨምሯል ይህንን ያክል ደርሳል የሟቾች ቁጥርም ጨምሯል የሚል ዜና ሲሰማ
😂እስረኛው በጭብጨባ ቿ ቿ በማድርግ ግቢውን ይቀውጠዋል ምክኒያቱም ወረርሽኙ ከጨመረ እንፈታለን😂የሚል ሐሳብ ይዘው ነውኮ።
✍️በወረርሽኙ ሰበብ የቤተሰብ ጥየቃ የለምና ማረሚያ ቤቱ የሚያዘጋጀውን ደያስ በማለት የሚጠራውን ሬሽን በመመገብ ጊዜውን መግፋት አማራጭ የለለው ነገር ነው።
✍️እንጀራው ጠርዙ ሰፊና ደረቅ ስለሚሆን የእንጀራ ቀበቶ ፍታ ይላል ዱርየው 😂ጠርዙን ጠቅልለው በመቁረጥ ያስወግዱና ሹሮ ነው ብለን የምናምነውን ሹሮ የማይመስል ወጥ ተጨምሮ ይበላል።
✍️በዚሁ የሲጅን ሐያትን ማሳለፍን መርጠናል።እድሜያቸው 20የማይሞሉ ሙስሊም ታሳሪ ልጆችን ከሱስ ለማራቅ እየሞከርኩና ሶላታቸው ላይ ጠንካራ እንድሆኑ ሲፈቱም የሒወት መስመራቸውን ያሻሽሉ ዘንድ ትችላላችሁ በዚህ መንገድ ሒዱ እየተባባልን በመመካከር ኑሮውን እየተላመድን ነው ምክኒያቱም ከገባሁ አመት እያለፈኝ ነበርና ምንም እንኳ በዱርዬ የተሞላ እስር ቢሆንም ምንም እንኳ ኢማን ለመጨመር ቀርቶ ያለህን የሚያሳጣ ዱርዬው በቲቪ የሚከፍተው ፊልም፣የሚጠቀሙት ጋንጃና ሲጋራ ቢኖርም ይህንን ሁሉ ታግሶ ማሳለፍ ግድ ነበር።
لا يُرفَع البلاءُ إلا بتوبة
ነውና የፈረጃው ቁልፍ።
✍️ቀኑ ለእስረኛ የዘገዬ ቢመስልም በጣም ረጅም ቀጠሮ ተሰጠኝ ብዬ የቆዘምኩበት ቀጠሮ ደረሰ።
✍️በቀጠሮዬ ቀን ልዴታ ከፍተኛ ፍርድቤት ቀረብኩ።ችሎቱ 1ኛ ፀረሽብር ችሎት ስለነበር ከእኔ ቀጠሮ ጋ ቀናቸው ተመሳሳይ የሆነ እነ እስክንድር ነጋም ቀርበዋል። የመጀመሪያ ችሎት የእነሱ ነበርና እኔ ቁጭ ብዬ ማዳመጥ ሆነ ስራዬ። ከእስኬ አባሪዎች አንድት ሴት ወጣት አለች አጭረ ናት ንግግሯ ግን እጅግ እሳት ነው።ከፍተኛ ችሎቱን ፍርሓት ትጥልበታለች በእርግጥ ልጅቷ በወያኔ ጊዜም ታስራ ነበር አሉ ያኔ በንግግሯ ሓይለኝነትና ጠንካራነት የተጨነቀ አንድ ዳኛ እኔ እዚች ልጅ ላይ ፍርድ አልሰጥም በማለት ችሎት ሰብሮ ወጥቷል ተብሏል።
✍️ቀጣይ ችሎት የእኔ ነው። አቅም የለኝም ጠበቃ አላቆምም ብልም መንግስት ጠበቃ መድቦሎኛል።ራሱ ከሳሽ ራሱ ጠበቃ አቋሚ ሆነና ነገሩ ይደንቃል።
✍️ለችሎቱ እኔ አሸባሪ አይደለሁም ክሱም ሐሰተኛ ክስ ነው ከእውነት የራቀ ነው።ከሳሽ ምንም አይነት መረጃ የለውም በማለት ለችሎቱ ከጠበቃው ጋ ለማስረዳት ሞከርኩ።ይቀጥላል

ወርቃማ ንግግሮች

28 Nov, 18:32


☔️ወደ ቀሶሳችን☔️

✍️ምንም እንኳ እስር ቤት ሕመሙ ከባድ ቢሆንም ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ካለፉት ከሌሎቹ የተሻለ ነው።ክላሶቹ ፣ውሓው መብራቱ ወዘተ ከሌላው የተሻለ ነው።
✍️ማታ 11ሰዓት ቆጠራ ተብሎ ወደቤታችን ተቆጥረን ከገባን በሗላ አልጋዬ ላይ ሆኘ ቁርኣን ለመቅራት እሞክራለሁ ከዛም ፉጡር ሲደርስ ከእኔ ጋ ሌሎች በእድሜ ትንሾች በሌላ ኬዝ የታሰሩ ልጆች ጋ ፕላስቲክ ዘርግተን በፍቅር እናፈጥራለን። ክላሱ ሰፊ ነው ቢያንስ 60ታራሚዎችን ይይዛል። ሶላታችንን ወደ አንዱ ጥግ ጠጋ ብለን በጀመዓ በመስገድ ሐዘናችንን ብሶታችንን ቀለል እናደርጋለን።
✍️ቀን ላይ ደግሞ የማረሚያ ቤቱ መፅሓፍት ገብቸ ኢስላማዊ መፅሓፍትና ኪታቦች አገኘሁ። በቃ ራስን ቢዚ ማድረጊያ ነገሮችን በማግኘቴ ደስተኛ ነበርኩ።
✍️የቀን ሶላቶችን ለመስገድ ትንሽ እንቸገር ነበር በፀሓይ ያኔ በድምፃችን ይሰማ ዘመን በ2008 አመፅ ተነስቶ ስለነበር ማረሚያ ቤቱ ሁሉም ዞኖች ያሉ መስገጃዎችን አፍሯሳቸዋል። ድጋሜም አልሰሯቸውም። መስጂዷ የነበረባት ቦታ ሊሾ ስለነበረች ፀሓይዋን ተቋቁመን ዝሁርንና አስርን እዛቹ እንሰግዳለን።
✍️በተለያየ ኬዝ የታሰሩ ወላሂ የሚሉ ታራሚዎችን በገራልኝ መልኩ ነሲሓ በማድረግ ጀመዓችንን ማጠናከሩን ቀጠልኩኝ።
✍️ረመዷንን በተለያዩ ውጣ ውረዶች አሳልፌ ዒደል ፊጥር ደረሰ😥ኣህህ በዚህ ወቅት ስሜቱ ድብልቅልቅ ነው የሚልብን። በእርግጥ ማረሚያ ቤቱ ለበዓላችን የተለያዩ ዝግጅቶችን ያደርግልናል። ለሁሉም ታራሚ ለስላሳ መጠጦች ይመጣሉ ድባቡም አብሽሩ እንኳን አደረሳችሁ በሚሉ የእርስበርስ የደስታ መግለጫዎች የግቢውን ድባብ ጥሩ መልክ ይሰጡታል።
✍️የዒደል ፊጥር ቀን ጧት ሻወር ወስደን ሁሉም ያለችውን ንፁህ ልብስ ለብሶ ቁርሱን በልቶ ኳስ መጫወቻ ሜዳዋ ላይ እንሰባሰባለን።
✍️መጥፎ ስሜት እንዳይሰማኝ ለማድረግ ብሞከርም በእስር ቤት ዒደል ፊጥርን ለመጀመሪያ ጊዜ ላሳልፍ ነውና አይን በእንባ ይሞላል ግን
👉እንባው እንዳይፈስ እከለክለዋለሁ
✍️የሚገርመው በሌላው ቀን የማይሰግዱትም በዒድ ቀን ፏ ብለው ሶፋቸውን ይዘው የዒድን ሶላትን ለመስገድ ይቀመጣሉ።
✍️እንደምንም አላህ ባገራልኝ መልኩ ኹጥባ ተዘጋጅቷል።ትንሽ ረፈድ እስከሚል ጀመዓውን ተክቢር እያስባልኩ እጅግ ሩቅ ስሜት ያለው ሰመመን ይዞን ተጓዘ።
በእርግጥም ጠበብቶች እንደሚሉት ነው
إذا كان الله معك فماذا فقَدت،
وإن فقدتَ الله فماذا وجدت
✍️ነዓም አላህ አንተ ጋ ከሆነ ምን አጣህ
እርሱን አጥተህስ ምን ታገኛለህ 😥
✍️ተክቢራችንን አንዴ ፈገግታ አንዴ ሲቃ እየተናነቀን
አላሁ አክበር አላሁ አክበር ላ ኢላሃ ኢለላህ አላሁ አክበር አላሁ አክበር ወሊላሂል ሓምድ ማለታችንን ቀጥለናል።
✍️የተወሰነ በተክቢራችን ቀልባችንን ካረጠብንና ኢማናችንን ጠንከር ለማድረግ ከሞከርን በሗላ።ለሶላት ቆምን
✍️አላህ ይቅር ይበለኝና እኔው ጃሒሉ የዒደል ፊጥር ሶላትን ለማሰገድ የመጀመሪያዋን ተክቢራ አላሁ አክበር በማለት ጀመርኩኝ😥 ነገር ግን ልቤ ቦታዋን ልትለቅ ትመስላለች ሰውነቴ መቆም እየተሳነው ይንቀጠቀጣል።እንደምንም ሶላቱ አለቀና የአላህን ታላቅነትና አዛኝነት ለዚህ ዐለም እዝነት እጅግ ባማረ አኽላቅ የላካቸውን አሽረፈል ኸልቅ صل الله عليه وسلم በማውሳት ቀኗን በምንም አይነት አሕዋል ላይ ብንሆንም በደስታ እንድናሳልፋት በመናገር የዒዱ ሶላትና ኹጥባን ጨርሰን በዓላችንን በደስታና ተሰብስበን ለማክበር ሁሉም በቻለው ከሱቅ የሚገዛው ይገዛል ፣ከካፌው ቡና ይታዘዛል በቃ ሁሉም እንደ አንድ ቤተሰብ ሁኖ ዒዱን ያከብራል።
ኢንሻ አላህ ይቀጥላል ።

ወርቃማ ንግግሮች

28 Nov, 18:31


☔️ወደ ቀሶሳችን☔️

✍️አንጋፋው ኢማም ሐሰን አልበስሪ رحمه الله እንድህ ይላሉ፦ሙእሚን እኮ በዱኒያ ውስጥ እስረኛ ነው።አንገቱን ከእስር ለማላቀቅ ይጥራል።በምንም ነገር አይተማመንም የተባረከውንና የላቀውን አላህ እስከሚገናኝ ድረስ ።محاسبة النفس لابن أبي الدنيا

👉የአገሪቱ ከፍተኛ ችሎት 1ኛ ፀረሽብር ችሎት በፕላዝማ ለመቅረብ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ያዘጋጀው ፕላዝማ ክፍል አጃቢዎች ጋ ገባን። እኔ ከመግባቱ ተከትሎ በነዛ ጀነራሎች ግድያ በነ ሳእረ ግድያ ተጠርጥሮ የታሰረው 10አለቃ መሳፍንትም በአጃቢዎች ክፍሉ ውስጥ ገባ። የዛሬ የፕላዝማ ቀራቢዎች ሁለታችን ብቻ ነን ማለት ነው። በእርግጥ መሳፍንት መሆኑን አላወኩም ነበር ስም ሲጠራና ክሳችን ሲነበብ ነበር የእሱን ኬዝና ስሙን ያወኩት። ፕላዝማው ተከፈተና ዳኞች ወደ ችሎት ወንበራቸው ተሰየሙ።ዳኞች እንደት አደራችሁ በማለት ነቃ ለማድረግ ከሞከሩ በሗላ ስማችን ተጠራና መቅረባችንን አረጋገጡ።
👉መጀመሪያ የመሳፍንት ችሎት ተጀመረና ክሱ ተነበበ።መሳፍንትም መልሱን ሰጠ ነገር ግን መሳፍንት ዳኞቹን የለለ ነው ከፍ ዝቅ ያደረጋቸው የመሓል ዳኛውን አንተ እከሌ ምናምን እያለ የሌለ ዛተባቸው 😂እንዴ አልኩኝ እኔ ዳኛ ላይ እንድህ ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ይቻላልዴ ብዬ ተገረምኩ። በእርግጥ አንድ አይኑ በዛ ክስተት ነው አሉ ጠፍታበታለችና ዳኞቹም ብዙም አልተቆጡበትም ሊያረጋጉት ሞከሩ። ብዙ ውርክቦችንና ዛቻወችን ካየን በሗላ የእርሱ ችሎት አለቀ።

👉ተከሳሽ ፉላን ተብሎ የእኔ ስም ተጠራና ከተቀመጥኩበት ወንበር ተነስቸ ወደ ማይኩ ጠጋ ብዬ ችሉቱ ቀጠለ።ዳኞቹ አድስ ናቸው ማለትም ከዛ በፊት አይቻቸው አላውቅም።
✍️ፉላን ይሰማል አሉኝ አወ ይሰማል ብዬ መልስ ሰጠሁና ወላጅና ወዳጅ ቢሰማው ራስ የሚያስተው ግብዳው ክስ መነበብ ተጀመረ። በጣም ብዙ ነገር አነበቡ። በቃ አለምን ዙሪያለሁ ኡማውን ለሸሪዓ የቀሰቀስኩት ይመስላል ክሱ።በእርግጥ ከነጮቹ የልዑኩ መሪ 17አመት አፍጋኒስታን ፣ኢራቅ ፣ሊቢያ ፣ሚስር ፣ሳዑድ አረቢያ አሸባሪዎችን መርምሪያለሁ እንደዚህ የራሳቸውን ማንነት ሳይቀር በመካድ ግግም የሚሉት የቡድኑ ግንድ ሆነው አግኝተናቸዋል ስለዚህ እንዳትለቁት የሚል መመሪያ ሰጥቷቸዋል።እኔ እንኳን ግንዱ የቅርንጫፉም ዘላል አይደለሁም።
✍️የፌደራል አቃቤ ሕጉ 3የሰው ምስክር ፣ቤት ሲፈተሽ የተገኙ ዶክሜንት የያዙ 4ፍላሾችና ቪዛ ነክቶት የማያውቀው ፓስፖርቴን እንደማስረጃ ክሱ ላይ አስቀምጧል።የሰው ምስክር የተባሉት አንዱ የፌደራል አባል በተያዝኩ ቀንና ቤት ሲፈተሽ በአካል የነበረ ቢሆንም ሁለቱ ግን የማያውቁኝ የማላውቃቸው የአድስ ከተማ ክፍለከተማ ነዋሪ ሰዎች ነበሩ።
✍️ክሱ ተነቦ ካለቀ በሗላ በቀጣይ መንግስት ከቀጠረልህ ጠበቃ ጋ ተነጋግራችሁ መልስ ትሰጣላችሁ በማለት የ2ወር ቀጠሮ ሰጥተውኝ ችሎቱን ለመቋጨት ተገደዱ ምክኒያቱም ፕላዝማው እየተቆራረጠ አስቸገራቸውና።
👉ከችሎት አጃቢዎች እኔንም መሳፍንትንም አብረው ይዘውን ወጡ።አይዞህ እንዳትፈራቸው አሸባሪው አለኝ በወታደር አነጋገር መሳፍንት። እኔም ፈገግ ለማለት እየሞከርኩ በግንባሬ እሽ አልኩትና እሱም የተመደበበት ዞን 5 እኔም ወደ ዞን 3 ገባሁ።
✍️መሕከማ ቀርበህ ስትመለስ እስረኛው አፉን አሹሎ ይጠብቃል ምን ተባልክ ለመቸ ቀጠሩህ ክስህ ተነበበ ወይ ብላ ብላ
✍️ረመዷን አሽረልአዋኺርም ግማሽ ሆኗል ቀጠሮየም ረጅም ስለሆነ ተረጋግቸ የቀረችውን የረመዷን ቀን መጠቀም አለብኝ በማለት ልብሶቸን አጣጥቤ ራሴን ፍሬሽ አድርጌ ከረመዷኔ ጋ ቁርኝቴን ጠበቅ አደረኩ። ይቀጥላል

ወርቃማ ንግግሮች

28 Nov, 18:31


☔️በዚህ መንገድ ነፍሳቸውን የሰጡትን እያየን ራሳችንን ስንንቅ በጠላት አይን ግን የእኛ ዋጋ ከባድ ነው☔️ይለኛል ጀግናው አቡ ፋሩቅ አማን አሰፋ اللهم فك أسره و فرج همه و يسير أمره

✍️በነገራችን ላይ እኔ ምንም አድርጌ አይደለም። በጠላት አይን ገዝፌ እንጅ ለዲነልኢስላም ምንም ያደረኩት ነገር የለም።አንድ ተራ ደካማ ፈቂር የጌታውን ምህረት ከጃይ ብቻ ነኝ።
✍️ብዙ የፈተና አይነቶች አሉ ይሄ መለኮታዊ ቁርኣናዊ ሕግ ነው። ብዙ እሾህ ወግቶኛል አሁንም መልኩን የቀየረ ፈተና አለ ግን የዱኒያን ቀድር ማወቅ ለሶብር ይረዳል።

✍️አባ ሳሙኤል የመጀመራያዋ ምሽት በረመዷን መጀመሪያ ቀን።ፖሊስ ኮሚሽን የተያዘ ፆም አባሳሙኤል አፈጠርኩ። ከፍጡር በሗላ ሶላቶቸን ሰገድኩና ገደም አልኩኝ።

✍️በስሁር ወቅት ተሳሓሩ የሚል የርቀት ድምፅ ሰማሁና ተነሳሁ።ውዱእ አድርጌ ውሓዬን ተጎንጭቸ ደገፍ ብዬ ቁጭ አልኩ። እንደምንም ነጋና ቆጠራ የሚሉት ቀውጢ ከእንቅልፍ የመደነባር ወቅት ደረሰ።

✍️ፖሊሶቹ የባንቧ ጎማ ወዘተ ይዘው ቆጠራ ቆጠራ ግው ግው የአላህ ምን ጉድ ነው አልኩኝ ።በቃ ከፊታቸው ያገኙትን እየወገሩ አስወጡን ቀላል አይማቱም ወላሂ። ምክኒያቱም ማንም የሚጠይቃቸው የለም ቤተሰብ ጥየቃ የለ ፍርድቤት መቅረብ የለ ኮቪድ ነው በቃ ትንሽ ከተገላመጥክማ አሸዋ ላይ ነው እያንከባለሉ የሚወግሩት 😥

✍️የረመዷን 2ኛ ቀን በአባሳሙኤል። ረመዷን በሚሆን ጊዜ ለፆመኞች ልዩ ምግብ ይዘጋጃል ቴምር ይመጣልና ፍጡር ሰዓት ሲደርስ ፆመኞች ወደ በር መጥታችሁ ሬሽናችሁን ውሰዱ ተብሎ ተቀበልንና ተከፋፈልን።

✍️ፀጉርህ እንዴት ነው የሚያምረው እያሉ አሟረቱብኝ መሰል 😂ፀጉር ያሳደግሽ ሁሉ ፀጉራችሁን ተቆረጡ ባለሙያ መጥቷል ካልሆነ ሌላ ነገር ነው የሚከተላችሁ የሚል የዛች ትእዛዝ ተላለፈልን። ሁላችንም ፀጉራችንን በወረፋ በሁለት ቀን አሳጭደን ጨረስን።

✍️በዚህ ሁኔታ አባሳሙኤል ለ21ቀናት ቆየን።ይህም 21የረመዷን ቀናት😥
✍️ኳራንታይን የሚገቡ አድስ እስረኞች ሊመጡ ነውና እቃችሁን ሸክፉ ወደ ቂሊንጦ ትሄዳላችሁ ተባለና እቃችንን ሸከፍን። እርስበርስ በካቴና እየጠረነፉ በቀረበው ባስ ተጪንና ወደ ቂሊንጦ።

✍️ቂሊንጦ ስንደርሶ ዞን 3 ግቡ ተባልንና።ዞኑ ውስጥ ባሉት 8አዳራሽ ክላሶች መደቡንና ካቦ ለዛሬ እርሱ ይሁናችሁ ብለው እኔን መረጡኝ ፖሊሶቹ።

✍️እረ ይሄ ደረሳ በማለት ዱርዬው አልተመቸውም ምክኒያቱም ከሹርጧ ጋ የሚጠጋጋ ሰው አይወዱም #አስጠጭ ነው የሚል ስያሜ አለ።ውስጥ ላይ ዱርዬው የሚሰራውን ፋወል ወሬ የሚያቀብል ማለት ነው አስጠጭ ማለት። በስለት ሊወጉትም ይችላሉ።
👉እኔ ከዚህ የጠራሁ መሆኔን የሚያውቁ ልጆች ለዱርዬወቹ አስረዷቸውና ቅሬታቸው ተስተካከለ።እኔም ካቦ አልሆንም ብዬ ከፖሊሶቹ ጋ ብጨቃጨቅም ሊሰሙኝ አልፈለጉም።

✍️በዚህ ሁኔታ ቀኑ ጥሷልና ያ ረጅም የመሕከማ ቀጠሮ ደረሰና የነገ ፍርድቤት ቀራቢዎች ተብሎ ስም ተጠራና በጧት እንድትወጡ ተባለ።
✍️ጧት ቢጫዋን መለዮ ለብሸ ወጣሁ አይ አንተ አትሄድም ከዚሁ በፕላዝማ ነው የምትቀርቀው አሉኝ🙄
👉በፕላዝማ ማለት አልገባኝም ለምን ስል በቃ ትእዛዝ ነው አሉኝ ውይ ይሄ ትእዛዝ
✍️ከፍተኛ ፀረሽብር 1ኛ ወንጀል ችሎት በፕላዝማ ተከሰትን
ይቀጥላል
ደህና እደሩ ግን

👉✍️👉 ብዙ ያልፃፍኳቸው ያለፍኳቸው አሳዛኝ አጋጣሚዎች አሉ። የሙስሊሙ ወኪል ነን ባዮች ምርመራ ቢሮ መጥተው አናግረው ኬዙን ሲያውቁ ስራቸው ያውጣቸው በማለት ወዳጆቻችንን ያስለቀሱ ታዋቂ አክቲቪስት ተብዬና አንድ ሁለት ሸይኽ ነገር አሉ።ያው ብዙም አያስፈልግም ብዬ ነው ያለፍኩት።

ወርቃማ ንግግሮች

28 Nov, 18:31


✍️ከሁለት የጎንደር ተወላጅ ፌደራሎች ጋ ከአድስአበባ ፖሊስ ኮሚሺን በሰርቪስ ጉዞ ጀመርን ወደ ቂሊንጦ። ነገር ግን የኳራንታይኑ ቦታ የገቡ 3ቀን የሆናቸው እስረኞች ነበሩና ቂሊንጦ ስንደርስ እዚህ ማን አምጡ አላችሁ ከላይ አልተነገረንም ብለውን ተመለስን።
✍️ፌደራሎቹ ወደ አለቆቻቸው ደውለው የተፈጠረውን ነገሯቸው።አለቆቹም የሚወስዱብኝን ቦታ ነገሯቸው።

✍️አባ ሳሙኤል ይባላል።በወያኔ የመጨረሻ ጊዜ አካባቢ የተሰራ አድስ እስርቤት ነው።ሕንፃው ሲሰራ ሰፋ አድርጋችሁ ስሩት እናንተም ልትገቡበት ትችላላችሁ ብሏቸው ነበር አሉ በቀለ ገርባ😂

✍️ይህ አስፈሪ ውስጥ ከገባህ ከሰማይ በስተቀር ምንም የማይታይበት እስርቤት እንደደረስን ፌደራሎቹ ፖሊሶቹን አናገሯቸው።አድስ ሰው አምጥተናል ሲሏቸው አናስገባም እነዚህ ኳራንታይን የጀመሩት ሳይጨርሱ አሉና መቸም እርስበርስ ደርቢ ናቸውና ተጨቃጨቁ ተጣሉ የሲጅኑ ፖሊሶች ከላይ ትእዛዝ አልደረሰንም በማለት ገገሙ።እዛው የለመድኩት ፖሊስ ኮሚሽን ይመልሱኝ ይሆን ብዬ አሰብኩ።
✍️ወቅቱ እየሮጠ ነው ፌደራሎቹም ተበሳጩና ለአለቆች ደውለው ቂሊንጦም አባሳሙኤልም አናስገባም አሉ ልንመልሰው ነው በማለት ነገሯቸውና መንገድ እንደጀመርን አይይ ተመለሱ እናናግራቸዋለን የሚል ትእዛዝ ተሰጣቸው።
✍️በጣም ተንገላታሁ ፌደራሎቹም አሳዘንኳቸው ፆመኛውን አሰቃየነው በቃ ፆሙን ፍታ ምግብ እናብላህ እምነታችሁስ አስቻጋሪ ነገር ላይ ማፍጠርን ይፍቅድ የለ አሉኝ የጎንደር ተወላጅ ክርስቲያን ናቸው። እዛ እርስበርስ ወገናዊነት ስላለ ለእኔ ወገናዊነት ተሰምቷቸው እኮ ነው።

✍️መግሪብ እየደረሰ ነው።ቂሊንጦ አምጡትና አሻራ ሰጥቶ አባሳሙኤል እኛው እንወስደዋለን ተብለው ቂላንጦ ወስደው አስረከቡኝና እቅፍ አድርገው ቻው አሉኝ ብዙ ጊዜ መሕከማ ስለአጀቡኝ ተቀራርበናልና።
✍️ቂሊንጦ አሻራውንም ተስዊሩንም ጨርሰው ወደ አስፈሪው አባሳሙኤል በፓትሮል ኡፍፍ ይች ፓትሮል ምናለ በሰርቪስ ቢወስዱኝ

✍️አባሳሙኤል ስንደርስ ፉጡር ደረሰ ነገር ግን ሬሽን ተሰጥቶ አልቋል። እስረኛውም ጭጭ አድርጎ በልቶ ጨርሷል።
✍️ፍጡር ሲደርስ ምግብ እንዳለ ሲሰማህ ትንጠራዘዛለህ ግን ምግብ አለመኖሩን ስታውቅ ደግሞ ነገሩ ውስብስብ ነው😂 ፖሊሶቹ አሁን ማፍጠሪያ ከየት ይመጣል ምን እናድርግ እያሉ ሲጨቃጨቁ ድንገት ከቂሊንጦ አመራሮች መጡ ለመሆኑ የየት አገር ልጅ ነህ ወሎየ ነህ ታስታውቃለህ ግን ወሎ የት ሲሉኝ ነገርኳቸው እንዴ የአገሬ ልጅ ሲል አንዱ ሌላው እኔ የተንታ ልጅ ነኝ ግባ አሁን ማፍጠራያ ገዝተን እናመጣልሓለን አሉኝ ኦኦኦ ምቾት

✍️የተመደብኩበት ክላስ ስገባ አልጋው ሙሉ ነውና ለዛሬ በቃ መሬት ላይ ተኛ አሉኝ 👉ደቦቃ እንለዋለን በሲጅን ቆንቋ።
✍️ወቅቱ ቢያልፍም ፍጡር ፖሊሶቹ በየአይነት ከሚሪንዳ ጋ አመጡልኝና አፈጠርኩ።الحمد لله
ይቀጥላል
እረ ይሄ ነገር በpodCast ይሁን ዋይ አያልቅምኮ

ወርቃማ ንግግሮች

28 Nov, 18:03


~

አዛን ተባለና ሰዓቱ ደርሶ ኢማሙ ብዙ ሰው ስላልመጣ ጥበቃ ቁጭ አሉ። በዚህ ጊዜ ሙዓዚኑ «ያ ሸህኽ እንቁም። አዛን የሚጠብቁት መጥተዋል። ኢቃም የሚጠብቁት ደግሞ እስኪደረግ እየጠበቁ ነው።» አላቸው አሉ።

አላህ ከብርቱዎች ከመልካም ነገር የተባለ ሁሉ ቀዳሚዎች ያድረገን።

ወርቃማ ንግግሮች

27 Nov, 18:42


እውነት / ሀሰት 
((1)) ሸሪአዊ እውቀት መፈለግ መማር ግዲታ ነው ??

ጥያቄ ትክክለኛው መልስ ሰታገኙ የሚያመጣላችሁን add አድርጉለት 👇

ወርቃማ ንግግሮች

26 Nov, 16:02


~


እናቴ ጎረቤታችንን ጨው እንዲያውሷት ስትጠይቅ ሰማኋት፡፡ እኔም በመገረም
"እናቴ በቤታችን እኮ በቂ ጨው አለ፤ ታድያ ለምን ጠየቅሻቸው"
አልኳት፡፡ እናቴም እንዲህ አለችኝ
"እነሱ ሁሌም የተለያዩ ነገሮችን ይጠይቁናል፤ እንደምታውቂም ድሀ ናቸው፡፡ ስለዚህ እነሱን ብዙ የማይጎዳ ነገር ለመጠየቅ አስቤ የመጣልኝ ነገር ጨው ነው፡፡ ይህን ያደረኩት እነሱ ላይ ጫና ለመፍጠር ሳይሆን፤ እኛም እንደምንፈልጋቸው እንዲሰማቸው ብዬ ነው፡፡ በዚህም የፈለጉትን ነገር እኛን ያለ ሀፍረት በቀላሉ መጠየቅ እንዲችሉ ያደርጋቸዋል ብዬ በማሰብ ነው፡፡"
ለሰዎች ሞራል ስትኖር እንዲክ!!

#የእናቶቻችንን እድሜ አላህ ያርዝምልን

ወርቃማ ንግግሮች

26 Nov, 04:48


ይህ ቻናል ለሙስሊሙ ማህበረሰብ ባጠቃላይ
እጅግ ጠቃሚ ቻናል ነው
ወደ ቻናሉ ተቀላቀሉ ዛሬ ባይጠቅማችሁ
ነገ ይጠቅማችኋል
👇
t.me/+SYGKSEYXv-kyNTQ0
t.me/+SYGKSEYXv-kyNTQ0

ወርቃማ ንግግሮች

23 Nov, 03:43


ነቢ (ሰአወ) በሰሀቦቻቸው ላይ የሚመጣን ፈተና አውቀውት በየአጋጣሚው ነግረዋቸው ነበር። እነሱም ብዙ ማብራሪያ አልጠየቁበትም። እየሰሙ በአብዛሀኛው የቀደር ጉዳይ ሲሆን ዝም ይሉ ነበር። አንዴ እሁድ ተራራ ላይ ነቢና ሶስቱ ሆነው ሳለ ተራራው ቢንቀጠቀጥ በእግራቸው ተራራውን መታ መታ አድርገው "ኡሁድ ሆይ ተረጋጋ፣ እላይህ ላይ አንድ ነብይ አንድ ሲዲቅ እና ሁለት ሸሂዶች አሉ" አሉት። ኡሁድም ተረጋጋ። ለኡስማንም (ረ.አ) ሌላጊዜ በዋሲጣ "ኡስማንን በጀነት አበሽረው ሆኖም (ዱንያ ላይ) በላ ያገኝሀል" በለው አሉት። ሰውየውም ሄዶ ኡስማንን ሲነግረው ኡስማን "ሀስቡነላህ ወኒእመል ወኪል " አለ። እኒህ ኸሊፋዎችም ይሁኑ ሌሎች ሰሀባዎች እጣቸውን እንደማይቀይሩት አውቀው የኖሩት ያቆያቸውን ያህል አላህ በሚወደው በመኖር ነው። እንጂ እጣቸውን ፈርተው ሲጨነቁ ወይም ሲሸሹት አልኖሩም። እንሽሽስ ቢባል ወዴት !

አሁን ይሄንን ጽሁፍ የምናነብ ሰዎችስ እድሜ ከሰጠን ወደፊት ከምናየው ውስጥ እርጅና እና የቤተሰብ ሞት ይገኝበታል። ዱንያ ላይ ያለ የትኛውም ዝምድና መጨረሻው ተራ በተራ መቀባበር ነው። ያንተ ቀብር ላይ ወንድሞችህ ልጆችህ ሚስቶችህ ይቆማሉ ወይ ትቆምባቸዋለህ። ትዳርም ብትለው መጨረሻው መለያየት ነው፣ ወይ በፍች ወይ በሞት። ይዘነው ያልመጣነው ሀብትም ሲቀር ለወራሽ ነው። እውቀትም ትጃጅበትና ይጠፋብሀል። ጉልበትም ይከዳል። እንዴት ያለው ጓበዝ ሲያረጅ አባባ እየተባለ ከዘራው ይፈለግለታል። የዱንያ እጣ ነውና ይህ ቀን ለሁሉም ይመጣል።

በዚህ ሁሉ ወጀብ የኛ ድርሻ የተሰጠንን ዛሬ ጀሊሉ በሚወደው መልኩ በምስጋና መኖር ነው። ስለሚመጣው አለም እና ሁኔታ የመወሰን ስልጣኑም አቅሙም የለንም። ልክ እንደገበሬው ...ፍሬ አገኛለሁ ብሎ ይዘራል። ያርማል ይኮተኩታል፣ ኸይሩን ምርቱን ይመኛል። የሱን ድርሻ ከመወጣት አይቦዝንም። ስለውጤቱ ግን በርግጠኝነት ሳይናገር "እኛ ዘርተናል አላህ ያውቃል" እያለ ይኖራል።

ብዙ ወንድም ስራ ሲይዝ ባሰበው ልክ ቤተሰቡን ሊረዳ ሳይችል ሲቀር የሚበሳጭ አለ። አንዳንዶች ሲያማክሩኝ ሚዛኔን ሳልስት "እነሱን በሀብት ማኖር የናንተ ድርሻ አይደለም" እላቸዋለሁ። የናንተ ድርሻ ጠንክሮ መስራት፣ አለማባከን፣ ለመርዳት አለመሳሳት፣ ወላጆችን ከሚስትና ልጅ ሀቅ ጭምር ማስቀደም መቻል ነው እላለሁ። ይህ እሳቤ እስካለ ድረስ ቤተሰቦች የሚኖሩበትን ደረጃ መወሰን ስልጣን ያለው ፈጣሪያቸው ነው። አንተ ሳትፈጠር ያኖራቸው ወደፊትም ያኖራቸዋል። የልጅ ድርሻ በቻለው ሁሉ እነሱን ማስቀደም፣ መልካም ፊት ማሳየት፣ በልጅነቴ እንዳዘኑልኝ እዘንላቸው እያሉ አላህን መለመን ነው። አምርረው ከተናገሩም በለዘብተኛ ቋንቋ ጌታቸውን አምርረው መጠየቅን እንዲላመዱ መንገር ያስፈልጋል እላለሁ። በዋናነት እናትና አባትን ኢማን ማላመድ፣ ከሽርክ እንዲጸዱ ማስታወስ፣ ኢባዳ ላይ ማበርታት በጣም አስፈላጊ ነው። ዱንያ ላይ ልባቸው ሲንጠለጠል ካየህ ስለ አኼራ ማስታወስ መዳኒታቸው ነው። የጌታቸውን ቂስማን መውደድንም ማበረታታት ጭንቀትን ይቀንስላቸዋል።

ለቤተሰብ ውለታ ከምለው አንዱ ችግርህን አለመንገር ነው። ከእኔ ልምድ ሌላው ቀርቶ ቤተሰቦቼ ልጅ ስወልድ ይሰማሉ እንጂ ሲረገዝ እንኳን አልነግርም። ሸክሜን ከጀሊል ውጭ አላወራም። ዱአቸው ብከጅልም በጅምላ አያጣኝም። በችርቻሮ መጠየቁ ማስጨነቅ ነው። ትዝ የሚለኝ ድግሪ ጨርሼ ወደ ቤት መሄጅያ ብር አልነበረኝም። በዚያ ዘመን ብነግራቸው እንደሚጨነቁ እኔን ለመርዳትም የሰው ብድር እንደሚከጅሉ አውቅ ነበር። የሆዴን በሆዴ ይዠ ሳለ እዚሁ ዩኒቨርስቲ 3 ዲፓርትመንት እንቅጠርህ ሲሉኝ Physiology Department መርጨ ገባሁ። እንጂ ጅማ ለመቅረት ሀሳቡም አልነበረኝም። ከቀረሁ በሗላ እንኳን በአባ ጅፋር ምድር እስካሁን አላህ አስመችቶኛል።

እንደው በደፈናው እዚህ ስለገባሁ፣ በዚያ ስለወጣሁ፣ ከና አከና ሳይባል አላህን አሳምርልን፣ ታረቀን፣ እለፈን እያሉ መኖር ብልሀት ነው።እንዲህ ስላደረኩ እንዲህ ሆነልኝ ማለትና ስኬትን ወደ ራስ፣ ውድቀትን ወደ ነገራት መውሰድ ሞት ነው። የኔኑ አይነት የህይወት ኡደት ተከትለው ከኖሩት ወንድሞች ውስጥ የሚስቱ ቤተሰቦች የገደሉትና ጀናዛውን ባለፈው ሳምንት የላክነውም ሆነ ከአመት በፊት ሚስቱን ቆራርጦ የገደለው መምህር ጋር ኡመር መስጅድ አብረን ስንሰግድ ነበር። በህይወት ስንክሳር ስለገጠማቸው እና እንዴት እንዳስተናገዱት የማውቀው ነገር የለም።

አላሁል ሙስተአን!

@Kha abat ♙ copy

ወርቃማ ንግግሮች

22 Nov, 18:25


🔠🔠🔠🔠

  

    

      
   ረ 

ገባ ገባ በሉ


🖋ርዕስ    ኹሹዕ ፊ ሰላህ ⚫️

🎙አቅራቢ ፦ ከማል አህመድ

የሚተላለፍበት ሊንክ

⬇️
t.me/tdarna_islam?livestream
t.me/tdarna_islam?livestream

ወርቃማ ንግግሮች

22 Nov, 11:37


🛜ዛሬ እና ነገ የሚደረጉ የዳዕዋ ፕሮግራሞች

ዛሬ ምሽት በትዳር እና ኢስላም ቻናል

t.me/tdarna_islam/4730
t.me/tdarna_islam/4730

ዛሬ ምሽት በኢብኑ ተይሚያህ ቻናል
⚫️
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/13943
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru/13943
⭐️
ነገ እለተ ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ
በደሴ ከተማ
🌟
t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy/19805
t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy/19805

🛜ከላይ ባለው ልንክ እየገባችሁ ሙሉ ተጋባዥ እንግዶች እና ርዕስ አንብቡ

ወርቃማ ንግግሮች

21 Nov, 15:37


☔️ወደ ቀሶሳችን
፨ለመከራ እጅ እንዳትሰጡ ነው።

✍️የፌደራል አቃቤ ሕግ የቅጣት አስተያየት አሰጣጥ ዳኞችን በጣም አስደንግጧቸዋል።እኔማ ደንዝዠ ነው የቆምኩት አጃቢ ፌደራሎቹም ደንግጠዋል።ምክኒቱም ከ15አመት እስከ ሞት ይፈረድበት ዘንድ ክቡር ፍርድ ቤቱን እጠይቃለሁ ነውኮ የተባለው ያ አላህ
✍️የመሓል ዳኛው ትልቅ ሰው ናቸው መነፀራቸውን ዝቅ አደረጉና በግርምት ተመለከቱኝ።በየወሩ እያደገ የሚያስቸግረኝ ፀጉሬ 6ወር አልተነካም በደንብም ተንከባክቤዋለሁ ሌላ ምን ስራ አለኝና😂ፂሜ ትንሽ ናት እንጅ የራስ ፀጉሬ ማሻ አላህ ሴት ያስቀናል ትላለች አያቴ ዳኛው ትኩር ብለው አዩኝና ተከሳሽ ለመሆኑ ከየት ነው የመጣሓው አሉኝ
✍️ከወሎ ኮምቦልቻ ነው አልኩኝ እስኪ ድገመው ሲሉኝ ከወሎ ደሴ ኮምቦልቻ አልኩኝ የበለጠ ለማብራራት። ታዳ ወሎ እነዚህ ከተሞች ላይ ሰው አልቋል ድርጅት ወድሟል ወይስ ምን አይነት ሽብር ፈፅሞ ነው በማለት ጨካኙን አቃቤ ሕግ ጠየቁት
✍️አቃቤ ሕጉም ክቡር ፍርድቤት እንደዛ አይደለም ተከሳሽ ከሶሻል ሚድያ ጀምሮ መሬት ላይ በርካታ ፊክሩን የሚከተሉ ሰወችን አፍርቷል ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት እያሰበ ነው በማለት አስረዳ።

✍️ዳኛውም ኣሓ እያሰበ ነው በሚል ክስ ነው ሞት ፍረዱበት የምትለው አሁን ይሄን ወጣት ብቻውን ከሳችሁ ሒወቱን ልታበላሹ ነው በማለት ተናገሩ።በእርግጥ ዳኛው አዝነውልኛል ከዛ ቀን በሗላ እኔ ችሎት ላይም አላየሗቸውም።

✍️በቀኝ ችሎት የተቀመጠው ዳኛ ተከሳሽ እከሌ ጠበቃ ማቆም ትችላለህ አለኝ እኔም አልችልም ይህ ክስ ሐሰተኛ ክስ ነው እኔ የተማርኩ ወጣት ነኝ ከራሴ ላይ እከላከላለሁ ብዬ በደነዘዘው አፌ ተናገርኩ።
✍️አይ ምንም እንኳ መከላከል ብትችልም ክስህ በጣም ከባድ ነውና አንተ አቅም ከለለህ መንግስት ጠበቃ ይመድብልሓል ስለዚህ
✍️ተከሳሽ በማረሚያ ቤት ሆኖ ክሱን ይከታተል ቀጠሮ ለግንቦት 17 ብለው ችሎቱ አለቀ።

✍️እኔም በቢጫው ኩርቱ ፌስታል የሚሞላውን ክስ ወረቀት ይዠ ከአጃቢዎቸ ጋ ወደ ሲጅን ተመለስኩ።
✍️በእርግጥ በደረሰኝ ፣ከዱባይ በጫማ ሚሞሪ ሻግ አድረገው ቦሌ ላይ ጋማ የሚባሉ ወዘተ ጉራጌና ስልጤ ሷሒቦች አፍርቻለሁ።ከቆጮ ፣አይቤ ፣ክትፎ ፣ቡላ ሳይቀር አስተዋውቀውኘ ከእነሱ የበለጠ የምግቦቹ አፍቃሪ ሆኘ ነበር።

✍️የክሱ ወረቀት ብዛት የገረመው በሆነ ኬዝ ታስሮ የዋስትና ብር አሰባስቤለት የወጣውና የፍርድቤት አጃቢ የሆነው የጅማ ተወላጅ ፌደራል አሁን ይሄን ክስ መች ተነቦ ነው መልስ የሚሰጠው በማለት በሐዘን ተናገረ።
✍️እንደማንም ወረቀቴን ያዩ ታሳሪዎች በጣም ደነገጡ ሸሹኝም የድሓን ኪስናቤት አውልቆ ነፍስ ቀጥፎ የገባው ወንበዴ ሁሉ ለካ እንደዛ በምርመራ ሲያጣድፉት የነበረው ለዚህ ነው አሸባሪ ነው ማለት ነው በማለት አጉረመረሙ።
✍️ግን ሰው ሲጠፋ እኔው ጃሒሉ የሲጅኑ የጀመዓው ኢማምና ኸጢብ ስለሆንኩ ደፍረው የሆነ ነገር ማድረግ አልቻሉም።አልሓምዱሊላህ

✍️የረመዷን የመጀመሪያ ቀን ነው ብያችሗለሁ ኮረና ስለነበር ቤተሰብ ጥየቃ ተከልክሏል ያለ ስሁር ነው የተፆመው። ከፍርድቤት መልስ ስሜ ተጠራና እቃህን ይዘህ ውጣ ወደ ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ተጓዥ ነህ ተባልኩኝ። በጣም ደክሞኛል የአቃቤ ሕጉ ንግግር አስደንግጦኛል ብርድብርድ ብሎኛልና ወርጀ ነገ ውሰዱኝ ብየ ብለምናቸው አሻፈረኝ አሉ ወረቀቱ ተፅፏል ምን እናድርግህ አሉኝ።
✍️ጓዜን ጠቅልዬ የሚወዱኝ ጀመዓውን በእንባ እየተራጨን ወዳኣን ተባብለን ተለያየን።
✍️ወቅቱ ኮቪድ እየተስፋፋ ነው ስለተባለ ለኳራንታይን ሌላ ቦታ ነው የምትሄደው ቂሊንጦ አይደለም ግን መጀመሪያ ቂሊንጦ ሔደህ አሻራና ትሰጣለህ አሉኝ።
ይቀጥላል

ወርቃማ ንግግሮች

21 Nov, 15:37


ነጫጭባዎቹ FBI ጋር ከጧቱ 3ሰዓት ጀምሮ 10ሰዓት ድረስ የምርመራ ጊዜ አሳልፌ ተመለስኩ። ልክ እስረኛው ጋ ስቀላቀል የት ወስደውህ ነው ወዘተ ጥያቄ እኔ ለራሴ የሕንፃው ቅዝቃዜ ድካሙናውሓ ጥሙ አንቀዋሎኛል። ቀጥታ ክላስ ገባሁና ምግብ ቀማምሸ አረፍ አልኩ።
✍️በዚህ በኩል አገር ቤት መጥፎ መጥፎ ወሬ እንደሚወራ ደረሰኝ። ኬዙ ከባድ ነው ሒዳችሁ አትጠይቁ ተባለ። እናቴን የሚናገራትም ቤተሰብ ነበር። ቤቱ ላይ ሳተላይት ነጥሞ ወዘተ
፨የአባቴ ቤተሰቦች እኛን ሊያጠፋ ነሷራን ሊዋጋ ልጅህ እንደዚህ ሆኖ ታሰረ እያሉ ጥላቻን ይሰብካሉ።አላህ ዐፊያ ያድርገውና አባቴም እኔን በማተቤ ሊዋጋኝ ብሎ በጣም እንደከፋውና እንደተቀየመ ሰማሁኝ።
✍️ብቻ አገር ቤት የሚወራው ያቆስላል ወላሂ።

✍️በሚቀጥለውም ቀን ስሜ ተጠራ እኔም ቀስ ብየ ዘግይቸ ወጣሁ በጣም ተናደው ስላልተመታህ ጠገብክ አይደል ብለው በጩኸት አንባረቁብኝና የተለመደውን ካቴና ሸብ አድርገው ምርመራ ቢሮ ገባን።

✍️ነጮቹ አሉ የፌደራል አቃቤ ሕግና የአምንያው ከፍተኛ ሰወች ጨቅ ብሏል ቢሮው።
✍️እ አሜሪካ ልንወስድህ ነው ሲሉኝ አቃቤ ሕጓ ቀጠል ብላ ከሚወስዱህ እውነቱን ተናገርና ከእኛ ጋ ስራ ሁሉም ነገር ይሟላልሓል ስትለኝ እኔ ንፁህ ሰው ነኝ እዛም አልሓዴም እዚህም መታሰር የለብኝም የሚል መልስ ሰጠሁና ፀጥ አልኩ።

✍️pc አዘጋጁና ቤቴ የተገኙትን ፍላሾች እየሰኩ እነዚህ እነማን ናቸው?ባንድራውስ የማን ነው? እያሉ ቆንጆ ቆንጆ ቪድዮዎችን አስኮመኮሙኝ ቀላል ሾፍኳቸው ሰፍ ብዬ ሳይ ይነግረናል ብለው ነበር መሰለኝ እነማን ናቸው ሲሉኝ
🙄አላውቃቸውም ነዋ የኔ መልስ።

✍️በጣም እየተጠጉ አጨናነቁኝ ለሐበሾቹ የሕግ ባለሙያወች ይህንን ልጅ እንዳትለቁት እያሉ ነጮቹ ይጮሓሉ።
✍️አላውቅም የሚል መልስ እየሰጠሁ ቀጠልኩኝ ነጮቹም You are liar እያሉ ሲቀውጡት
፨እንግሊዘኛ አልችልም ያልኩት እኔ እረ እኔ ውሸታም አይደለሁም አልልም 😂😂😂 ቀላል አልሳቁብኝም ወላሂ

✍️የተለያዩ መስቀለኛ ጥያቄዎችን አቅርበው አልተሳካላቸውም ከቢሮ ወጣሁ።
✍️4ኛው ዙር ማለትም የ4ወር የእስር የምርመራ ቀጠሮ ደረሰና አሁንም መሕከማ ሔድን።መርማሪ ብዙ ወሬ ዘበዘበ ሌሎች ያልተያዙ መረጃዎችና አባሎች አሉት ጊዜ ይሰጠኝ ሲል ዳኛው አይ 4ወር ሙሉ ምንም በቂ ነገር አላመጣችሁም በ15ቀን ውስጥ አቃቤ ሕግ ክስ ካልመሰረተ እስረኛው በነፃ እንድለቀቅ መዝገቡ ተዘግቷል ወደ መዝገብ ቤት ተባለና ወደ ሲጅኔ ተመለስኩ።

✍️ለአንድ ወር ቀጠሮ የለ ምርመራ የለ ፀጥ ፀጥ አይ ጭንቀት ለካ መሕከማውም ምርመራውም እፎይታ አለው አልኩኝና ሐሳብ ያዘኝ መጨረሻ ቀናቶች ላይ ወደ ቢሮ ተጠራሁና በሊፍት ወደ መጨረሻ ፎቅ ይዘውኝ ወጡና ሙሉ አሻራ ነጠቁኝ።
✍️የረመዷን የመጀመሪያ ቀን ስሜ ተጠርቶ ልደታ ከፍተኛ ፍርድቤት ቀጠሮ አለህ ተባልከኝ አላህ አላህ በቃ ከሰሳችሁኝ ብየ ለባብሸ ወደ ልዴታ
✍️ከፍተኛ ፍርድቤት ቀርቤ 1ሺ300አካባቢ ወረቀት የሚሆን ክስ ተሰጠኝና
👉አቃቤ ሕግ ክሱን መናገር ጀመረና ክቡር ፍርድቤት ልጁ መካከለኛው ምስራቅ ድረስ እጁ ረጅም ነውና
✍️ከ15አመት እስከ ሞት ድርስ ይፈረድበት ዘንድ እንጠይቃለን አለ😥በቃ እንደቆምኩ ደነዘዝኩ .....

ፎቶዋ ነፃ የተባልኩ ቀን አንድ ሷሒቤ አላህ ይቀበለውና ያነሳኝ ነው ነሓሴ10/12/2013

ወርቃማ ንግግሮች

21 Nov, 15:36


✍️የመጀመሪያው የ28ቀን ቀጠሮ ደረሰና ወደ ፍርድቤት ወሰዱኝ ግን አሁንም ተመሳሳይና ትንሽ ይዘቱ የተለየ ሐተታ መርማሪ አነበበ ምን ትላለህ የሚለው የዳኛ ጥያቄ ወደእኔ ሲመጣ ከመጀመሪያው ተመሳሳይ ነገር ተናገርኩና አሁንም ድጋሜ የ28ቀነ ቀጠሮ ተሰጥቶ ተመለስን።

✍️ከጧትም ከሰዓትም ቢሮ ትፈለጋለህ የሚለው ጥሪ ስልችት ያደርጋል። ምርመራ ቢሮ ገብቸ በጥያቄ ማፈጠጥ ይጀምራሉ።ጉልበቴ ላይ ሊቀመጡብኝ ነው እንዴ እስከምል ይጠጉኛል ከፊት ከሗላ ከቀኝ ከግራ በቃ ወከባ ይፈጥራሉ።
✍️አላውቅም የሚለው መልሴ ሰልችቷቸዋል ለመማታት ይሞክራሉ ግን ጊዜው የአብይ ጊዜ ነው ለውጡ የሚባለውና መደብደብ ሙሉ ለሙሉ ባይቀርም የሽብር ተከሳሽ ላይ ግን የለም። ሌላው እስረኛ ግራ ተጋብቷል የዚህ ልጅ ኬዝ ምንድን ነው በየሰዓቱ ምርመራ የሚጠራው እያሉ ያወራሉ። እኔም እጅ እጅ ብሎኛል።

✍️የረሳሁት ነገር ከእስረኞች ጋ ስቀላቀል የግርግዳ ስልክ ስለነበር ለቤተሰብ ደውዬ እንዳሳውቅ ተፈቀደልኝና

✍️ሔሎ ስል አቤት ፉላን ነኝ ስል እ አለህ በሒወት 😥የሚል መልስ አወ አለሁ እንድህ እንድህ ቦታ ነኝ ብዬ አሕዋሉን ተናገርኩኝ። الحمد لله

✍️ስሜ ሲጠራ ከመሰልቸቴ የተነሳ የሚጠይቀኝ ሰው መጥቶ ሲያስጠሩኝም ለምርመራ እየመሰለኝ በቃ ቸልተኛ እሆናለሁ ሌላ ሰው ወርዶ እረ ቤተሰብ ነው ተብዬ እወርዳለሁ

✍️በዚህ እየቀጠልኩ 3ኛ ወር የእስር የምርመራ ጊዜ መካከል ላይ አንድ ቀን ከጧቱ3ሰዓት ስሜ ተጠራና ቢሮ ትፈለጋለህ ተብዬ ወጣሁ። የዛሬ አጃቢ ፌደራሎች ብዙ ናቸው አድስም ናቸው የሕንፃው ድባብ ያስፈራል።

✍️ምርመራ ቢሮ እንደደረስን በሩ ተከፈተና ልክ ስገባ 3 ነጮች ቆመዋል።እረ አንተ ልጅ ምን እየተካሄደ ነው በቃ አለቀልኝ ጉዳዩ ከባድ ነው ብዬ አሰብኩ።

✍️ወንበር ላይ ተቀመጥ አለኝ ከኢምባሲ ለትርጉም የመጣ ጉዙፍ ሰውዬ። ወንበሯ ላይ ቁጭ ነጮቹ ሰዎች እንዳልኩ ጠረንፔዛ ላይ የሆነ ማሽን ነገር አውጥተው አስቀመጡና ከተነጋገሩ በሗላ ምን እንዳደረጉኝ የማላውቀው ስሜት ተሰማኝ ራሴን በጣም አመመኝ አይኔም ብዥ አለብኝ ደንግጬ ፊቴን በታሰረው እጄ ለመዳሰስ ሞከርኩ 😥

✍️በዛ ሁኔታ እያለሁ አንዱ ፈረንጅ Hi ፉላን ብሎ ማኖ ሊያስነካኝ በሆነ ስሜ ጠራኝ እኔም ራሴን በጣም እያመመኝ ነውና እንደምንም ራሴን እያረጋጋሁና እንዳልሸወድ እየጠርኩ Hi ስሜ እከሌ ነው አልኩኝ። እሱን ተወው አይነት ሹፈት አሾፉብኝ

✍️ውጭ ጠብቅ ብለው አስወጡኝና ነጮቹ ከሐበሻ መርማሪዎች ጋ ሲጨቃጨቁ ቆይተው ድጋሜ አስገቡኝ።

✍️እርስበርስ እየተያዩም እርሱ ራሱ ነው ተባባሉ። ተርጎሚው ሰውዬ ከጎኔ ነጮቹ ከፊት ለፊቴ በጠረንፔዛ ዙሪያ ተቀመጥንና ራሳቸውን አስተዋወቁኝ።

✍️እኛ አለም አቀፍ ሽብርተኞችን የምንመረምር ከአሜሪካ የመጣን የFBI ሰዎች ነን አሉኝ። የመደንጥ ስሜት ተሰማኝና ዝም አልኩ። የሚጠጣ ጠጣ ብለው ኮካ ሲሰጡኝ አይ አልፈልግም አልኩኝ። ማን ያውቃል ኮካ ይሁን ሌላ አሜሪካ አይደለች የላከቻቸው

✍️እንግሊዘኛ ትችላለህ ሲሉኝ አልችልም በማለት መለስኩ። ትችላለህ ቀጥታ መልስ ትሰጣለህ ብሎ በክርኑ ጎኔን ወቀረኝ ብዙም አልጎዳኝም ግን
✍️ያች ማሽናቸው ምን እንደሆነች አላውቅም ራሴንና አይኔን ሕመም ፈጥራብኛለች።ጧት 3ሰዓት የተጀመረ ምሳ ሰዓትም አለፈ እያስጨነቁኝ በመጨረሻም

✍️አሜሪካ ብትታሰር ይሻልሓል ወይስ🙄 እዚሁ የሚል ዱብዳ ጥያቄ ጠይቀው ከምርመራ ቢሮ አስወጡኝ።
✍️እስረኛው እየተጠባበቀ ነበርና ብቅ ስል ያ አላህ በደስታ 😍የማያውቅህ ሁሉ ይጨነቃል ለካ የመከራ ቦታ አንድ ሲያደርግህ።
......
🙄እንዴ አሜሪካ

ወርቃማ ንግግሮች

21 Nov, 15:36


☔️ እንዴት አደራችሁ ጀመዓው አሰላሙ ዐለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱ
፨ከጥቂቷ ታሪኬ ቅመሱ

✍️ከፍርድ ቤት መልስ ራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩ።ከወንድሞች የታለከልኝን ነገርም ቀማመስኩና ረፍት እንድሰማኝ ለማድረግ ከነፍሴ ጋ ትግል ይዣለሁ። ነገር ግን እሁድ በጧት ወስደውታል ከሚል የፖሊስ ጣባያ መረጃ ውጭ የት እንደገባሁ የማያውቁ ወዳጅቤተዘመድ ገድለውት ይሆን ወይስ በሒወት ይኖር ይሆን በሚል ሐዘን ውስጥ እንደሚሆኑ ሲስማኝ በጣም ውስጤ ተረበሸ።
✍️በዚህ መሓል እያለሁ በ4 መእዘኗም ካሜራ የተገጠመላት ጠባቧን ክላስ እየቃኘሁ ሁሌ የምወደው የወንድም
ኸውላን ሰንዓኒ ተቀበለላህ ሺዕር ታወሰኝና እርሷን ደጋግሜ በማለት ውስጤን ተሽጂእ አደረኩኝ።
ሺእሯም እንድህ ትላለች

هي الدنيا ورب البيت تفنى
فهبوا للجنان مشمرينا

أحبتنا شممنا المسك فيهم
ونور الوجه لم يبدو حزينا

كأن الحور قد نادت وقالت
هلم ايا حبيبي للسكينة
በድምፅ እንድልለት የፈለገ በውስጥ ያናግረኝ።😂

✍️ሺዕሯን እየቀወጥኩ ድንገት 8ሰዓት ከ30አካባቢ ስሜ ተጠራ እህ አሁንም መህከማ ሊወስዱኝ ነው ብዬ ግራ እንደተጋባሁ ፖሊሶች መጡና በሩን ከፍተው ይዘውኝ ወጡ።ፖሊሶቹ ለፌደራል አስረከቡኝና እጄ በካቴና ታስሮ ወደ ፎቅ ወጣን።
✍️አስፈሪ ሰዎች የሞሉበት ቢሮ ይዘውኝ ገቡ ከዛ በመጨረሻም እጃችን ገባህ ኣ በዚህ በለውጥ ዘመን ደግሞ ምን ልሁን ብላችሁ ነው ያኔማ ቢሆን የተያዝከው እንድህ በሰላም ምርመራ አይደረግም ነበር ወዘተ እያሉ አዋከቡኝ። ኣሃ ምርመራ የሚባለው ነገር እየተጀመረ ነው አልኩኝ ለራሴ።

✍️ቅስምህን ለመስበርና ሚስጥር ለማጋለጥ ተስፋ ለማስቆረጥ ስለሚፈልጉ ዘለው አሁን አንተ በዚህ እድሜህ 15አመት ተፈርዶብህ ጨርሰህ ስትወጣ ሰው ትሆናለህ? የሚል የሹፈት ቃል ይናገሩሓል በቃበአላህ መመካት ብቻና ፅናት እንድኖርህ መታገል ብቻ ነው በዚህ ቅፅበት አማራጭህ።

✍️ምርመራው ተጀመረ ስም ተመዘገበ ለነገሩ ብዙ ስም ነው ያለህ የሚል ማሽሟጠጥ 😂 እንደማንም አንዴ በቁጣ አንዴ በመለሳለስ የተለያዩ ጥያቄዎችን እየጠየቁ ለማፋጠጥ ሞከሩ። እኔም አላውቅም የሚልን መልስ በመስጠት ግግም አልኩ። አላውቅምን ተለማመዱ የብዙ ሸር በሮችን ትዘጋለች ትል ነበር አያቴ።

✍️ውሰዱት ተብለው ፌደራሎቹ ይዘውኝ ወረዱና ካቴና ተፈቶ ለፓሊሶቹ ማንም ጋ እንዳይገናኝ የሚል መመሪያ ተሰጣቸው።
✍️ጨለማ ክላሷ ጠባብ ናት በዚህ ላይ ጧት 2ሰዓት ለሽንት ይከፈትልኝና በ20ደቂቃ ውስጥ ጣጣየን ጨርሸ እገባለሁ ይቆለፋል ማታ 11ሰዓት ለተመሳሳይ ነገር ይከፈታል በቃ እንድህ ነው።ፀሓይ አይታይህ መምሸቱ አያስታውቅ።ድምፅ ብቻ ነው የምትሰማው።

✍️የሶላት ወቅቶች ሲደርሱ የኖርማል እስረኛ ጀመዓዎች አዛን ይሰማል በማይክ ከሚደረገው የበለጠ ያምራል ሕንፃው ኢኮው ደስ ይላል ያስተጋባል። አይይይ ብዬ ስሜን ጠርቸ ምናለ ከሌሎቹ እስረኞች ጋ በሆንኩ ብዬ ተመኘሁ። ምክኒያቱም ፍርድ ቤት ላይ መርማሪ ፖሊስ 28ቀን የምርመራ ጊዜ ጠይቆ ስለተሰጠው ረጅም ጊዜ እንደምቆይ አውቂያለሁ።

✍️መሸ ነጋ አጣዳፊው ምርመራ ከጧትምከሰዓትም ቀጥሏል ስሜ ሲጠራ እስከሚያስጠላኝ ድረስ። ከዛ አንዱ ፌደራል አትሰልች ገና መቸ ተነካና በዚህ የምርመራ ሒደት 4ወር ይቀጥላል ብሎ ቁርጤን ነገረኝ በረካ ይሁንና።

✍️ተደጋጋሚ ምርመራ ከተደረገ በሗላ ምንም የሚያገኙት መረጃ ሲያጡ ተበሳጩና ብቻውን ሆነ አልሆነ ምን ጥቅም አለው የመከረው ሰው አለ ማለት ነው የት ምናምን እያሉ ይጨቃጨቃሉ። እኔ ምን አገባኝ አላውቅምን ሙጭጭ ብያለሁ።

ወርቃማ ንግግሮች

20 Nov, 09:16


የስራ ማስታወቂያ የምንለቅበት
አዲሱ  ⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️ ነው 
በሀገር ውስጥም ይሁን ካሀገር ውጪ ያላችሁ
የሱና ወንድም እና እህቶቻችን 
ይህ ቻናል ይጠቅማችኋል ተቀላቀሉ
👇
join request የሚለውን በመጫን✅️
t.me/+SYGKSEYXv-kyNTQ0
t.me/+SYGKSEYXv-kyNTQ0

ወርቃማ ንግግሮች

20 Nov, 02:29


"አንዲት ቅጠል አትወድቅም አላህ ቢያቅ እንጂ"

እንዴት ታዲያ ይሁ ሁሉ መልካም ነገር በልብህ የያዝከውስ?

ለሰወች የያዝከው ይህ ሁሉ ውዴታስ..?
የሰወች ስኬት የራስህ ስኬት ያህል የምትደሰተው ደስታህስ!
የሰወች ህመም ህመሜ ብለህ የምትታመመውስ ?
ወዳጄ :- አላህ እኛን ከላይ ያለንን አይመለከተንም ። አላህ የሚመለከተው ውስጣችንን ነው ።

ንጉሱ የሚመለከተውን ክፍል አሳምረው
በአካል ውስጥ አንዲት ስጋ አለች እሷ ከተስተካከለች ሙሉ አካላችን ተስተካከለ እሷ ከተበላሸችም ሙሉ አካላችን ተበላሸ
እሷም ልብ ነች!

ወርቃማ ንግግሮች

19 Nov, 17:21


✍️ማእከላዊ የፌደራሎች ካምፕ ደረስን። ሻንጣ አይገባም በፌስታል አድርግ ልብስህን ተባልኩና አንዳንድ ደግ ወታደሮች ፌስታል ገዝተውልኝ ልብሴን በፌስታል ይዠ ወደ አድስአበባ ፓሊስ ኮሚሽን አመራሁ። ሰዓቱ የኢሻ አዛን እየወጣ ነበር።
ፌደራሎቹ ለአድስአበባ ፖሊስ አስረክበው ከጨረሱ በሗላ ቻው ብለውኝ ሔዱ።

✍️የአድስአበባ ፖሊስ ጋ ፍጥጫ ተጀመረ። ቅዳሜ ምሳ የበላሁ ነኝና ብርዱም ረሓቡም በጣም አድክሞኛል። ፖሊሶቹ ልብሴን ፈተሹ የጀለቢያ አላባሽ ቱታዎቸን ገመዶቻቸውን መንጥረው መዘው አወጡ።ስም ሲመዘግቡ ክልል ሲሉኝ አማرا ስል በግልምጫ ኮስተር አሉ ዞን ሲሉ ወሎ ስል ትንሽ ሞተር አቀዘቀዙ። እርቦኛል የሚበላ ስጡኝ ስል ክፉ ቃል ተናገሩኝ ትንሽ ባሰኝና የድካም እንባ መጣ

✍️ኬዙ ከባድ ነው ልዩ ጥበቃ አድርጉ ጨለማ ቤት አስገቡት የሚል የስልክ ትእዛዝ ተሰጣቸውና መብራት እያለው ግን ጨለማ የሆነ የሚጨንቅ 4ማእዘን ላይ ካሜራ የተገጠመለት ግራውንድ ክላስ አስገብተው ወረወሩኝ።

✍️መግሪብና ኢሻን ቂብላውን ሳላውቅ በብርድና በረሓብ በደከመ ሰውነት በደመ ነፍስ ሰገድኳቸውና ብርድ ልብሴን ደርቤ ጎኔን አሳረፍኩ።ምንም እንኳ በጣም የረሓብ ስሜት ቢሰማኝም ብርዱ ሰውነቴን ስላደነዘዘው እንቅልፍ ወሰደኝ።የሆነ ሰዓት ላይ ነቃሁኝና ረጅም ሰዓት የተኛሁ ስለመሰለኝ ፈጅር ይደርሳል እስካሁን ብዬ ተየሙም አድርጌ ሰገድኩኝ።ትንሽ አዝካር ለማለት ሞከርኩና ግርግዳውን ተደግፌ ቁጭ አልኩኝ።እንደምንም ነጋና ጧት ፍርድ ቤት ሊያቀርቡኝ ስሜ ይጠራል በሩ ስለተቆለፈ ብሰማም ምንም ማድረግ አልቻልኩምና ዝም አልኩኝ። የተወሰነ ሰዓት በጥሪ ከደከሙ በሗላ ማታ ጨለማ ቤት ያስገባነው አድሱ እስረኛ ነው ብለው አስታውሰው መጡና ከፈቱልኝ ስምህ ሲጠራ አትሰማምዴ ብለው ጮሁብኝ ብሰማስ ምን አደርጋለሁ የተቆለፈ ክላስ ተቀምጨ አልኳቸው። በል አሁን መፀዳጃ ከፈለክ ግባና ተጣጠብና ውጣ ወደ ፍርድ ቤት ልትሄድ ነው አሉኝ።
✍️በተያዝኩ በሳምንቱ ሰኞ አድስአበባ አራዳ ፍርድ ቤት ቀረብኩ።መርማሪ ፖሊስ ተብየ ወረቀት ተሸክሟል። ስሜ ተጠራና ችሎት ቆምኩ መርማሪ ፖሊስ በዛ ወጥቶ በዚህ ወርዶ ወወወ የሚል እጅግ ብዙ ነገር አነበበ በቃ ቢላደንን የያዙ አስመሰሉት በዛ ሒዶ ወጣት እየመለመለ እንትና ከተማ ሴል እያዘጋጀ ከእንትን አለም አቀፍ የሽብር ቡድን ጋ ጥብቅ ትስስር በመፍጠር ኢስላማዊ መንግስት ለመመስረት ወዘተ በቃ ኡፍፍፍ።ዳኛው ምን ትላለህ አለኝ ስለምኑ ነው የምናገረው አልኩት ስለተነበበው ክስ አለኝ ይህ ክስ ለእኔ ነው ስለው ቆጣ ብሎ የምትናገረው ካለህ ተናገር አለኝ።እኔ ስለተነበበው ነገር የማውቀው ታሪክ የለም ከዚህ ነገር የጠራሁ ንፁህ ሰው ነኝ።ሒወቴን አታበላሹት የሐሰት ክስ ፅፋችሁ ወዘተ ብዬ ለፈለፍኩ የሚሰሙኝ መስሎኝ።
✍️መርማሪ ፖሊስ ተብየው 28ቀን የምርመራ ጊዜ ይሰጠን ብሎ ጠየቀ ተሰጠውና ከችሎት ወጣን።
✍️ሌሎች ታሳሪዎች ጋ በሰርቪስ ስንመለስ የት ነህ መች ገብተህ ነው ብለው ሲጠይቁኝ ጨለማ ቤት ነኝ ማታ ነው ያመጡኝ ብዬ ነገርኳቸው። አይዞህ ምን እንላክልህ ሲሉኝ ረሓብ ክፉ ነውና መሶበር አልቻልኩም
👉የሚበላ ነገር ካለ 😥ላኩልኝ አይኔ እየደከመብኝ ነው አልኳቸው።
✍️በዚህ መልኩ እዛች ጨለማ ቤት ተመለስኩ ወቅቱ ሐጂ ሰዒድ ያሲን የታሰረበት ጊዜ ነበርና ፍርድቤት ያገኙኝ ልጆች ሐጅ እረ አንድ የወሎ ልጅ ጨለማ ቤት አለ ምግብ ይፈልጋል ሲሉት ከምግብ መርጠው ምርጡን ከውሓ ጋ ላኩልኝ። ሰኞ ከሰዓት ምግብ ቀምስኩና ጌታዬን አመሰገንኩ። ይቀጥላል

ደህና እደሩ

ወርቃማ ንግግሮች

19 Nov, 17:20


የፖሊስ ጣቢያው ኮማንደር አሳልፌ አልሰጣችሁም ልጁን የምናውቀው በመልካም ነው ሲላቸው እርስበርስ ተጣሉና ሳይሳካ ቀረ።
✍️ሐሙስ ከሰዓት ከላይ ለኮማንደሩ ቀጭን ትእዛዝ ተሰጠው መሰል ጁሙዓ ጧት ፌደራሎቹ መጡና ውጣ አሉኝ።ልብሴን ሸክፌ ወጣሁ።

✍️👉ፌደራሎቹም በፕሌን ነው የምንወስደው ለሒወታችን መንገድ ላይ እንሰጋለን አሉ።ትኬት ተቆርጧል😂
የሆነች ጀግኖች የሚበዙባትን ከተማ ፈርተው ነውኮ ።
✍️ጁሙዓ ጧት ፖሊስ ጣቢያው በወዳጆቸ ተጥለቅልቋል በፌደራል የታጀቡ ፓትሮሎች ቀርበዋል እጄ በካቴና ታሰረና ፓትሮሉ ላይ ተጫንኩኝ። ወዳጆቸ ወደ ቀብር የሚሸኙኝ ይመስላል መሪር ሐዘን አለቀሱ። ይች ወቅት ትንሽ ለሕሊና ትከብዳለች
እኔው ተሽዬ ፓትሮሉ ላይ ሆኘ አብሽሩ አታልቅሱ አላህ በቂያችን ነው በማለት ለማፅናናት ሞከርኩ ግን የወዳጆቸ እንባ ከባድ ነበር።ራሳቸውን ስተው የወደቁ ሷሒቦች ነበሩ። አላህ ሐያታቸውን በደስታ የተሞላ ያድርግላቸው።አሚን

✍️ፓትሮሎ ተነስቶ ወደ ኤርፖርት ተጓዘ ሕዳር ወቅቱ ዝናባማ ነውና እዛ ስንደርስ በረራ ላይኖር ይችላል ተባለ።በቃ እጄ በካቴና እንደተጠረነፈ ብርድ ላይ ተወዳጇን ጁሙዓ ኤርፖርት አሳለፍኩት።10ሰዓት ሲሆን የበረራው ነገር እንዳልተሳካ ከበላይ አካል ሲነገራቸው ፌደራሎቹ ይዘውኝ ሌላ ፖሊስ ጣቢያ ወሰዱኝ።

✍️ጣባያ ከጣባያ ለምንድን ነው የምታንከራትቱኝ አለመሄዴን ለወዳጆቸ ልናገር ስልክ ልደውል ብዬ ስጨቃጨቅ ከየት እንደመታኝ የማላውቀው ጥፊ ጆሮዬን ሕው አደረገው አላህ ይምታህ አቦ ብየ ዝም አልኩ።እንደማንም ሰው ሰምቶ ቅዳሜ አለሁበት ጣቢያ ቁርስ ምሳ ወዘተ አመጡልኝ ።

✍️አሁንም ቅዳሜን ከዘያሪዎቸ ጋ አሳለፍኩት። ሌላ ቦታ ሆኖ ሚድያ ላይ ፎቶየን ያየ ወንድም ለእናቴ ደውሎ ኸበሩን ሲነግራት ቀኑ ጨለማ ሆነባት። ለቤተዘመዱ ስትናገር ሁሉም በድንጋጤና በፍርሓት ተጨንቋል ግን ይህን ሓይማኖት ማጠባበቅ ተው ብለነዋል አልሰማ ብሎ ነው ወዘተ ወሬ ተጀመረ።ነባሮቹ ዝም ያሉትን እርሱ ከቀሳውስት ቤት ተወልዶ አጉል ቃልቻ ነኝ አለ ተብያለሁም 😂

✍️ቅዳሜ ለይሏን ለእሁድ ልታስረክብ በቀረበችበት ለይል 10ሰዓት የታሰርኩበት ክላስ ተንኳኳና ተነሳሁ። ምንድን ነው ስል ውጣ የሚል ድምፅ ሰማሁ አልወጣም በዚህ ሰዓት መግደል ከፈለጋችሁ እዚሁ ግደሉኝ በማለት ጭቅጭቅ ተፈጠረና ፈጅር ደረሰ።
ወደ አድስአበባ ማእከላዊ ሊወስደኝ የመጣው የፓትሮሉ ሹፌር እና ዋና ክትትሉ ሶላት ይሰግዳሉና ፈጅር ሰግደን እንጓዝ ለአንተም ይሻልሓል ከፓትሮል ላይ ተጭነህ ከዚህ አድስአበባ መንገዱ ከባድ ነውና በጧት እንጓዝ መሄድህ ላይቀር አሉኝ።ፕሌኑ በቃ ቀረ 😂 ከአየር ላይ ሳይጥሉኝ ሆ

✍️እሁድ ጧት ከፓትሮል ወንበር ጋ እጄ ወደሗላ ተጥርንፎ ጉዞው ተጀመረ። እናቴ በዚሁ ቀን ከኩታበር ሰው ተከትሏት ከተማው ደርሳ ስትጠይቅ ልጄን ስትል የተረገሙ ፖሊsoች ለሊት ነው የወሰዱት ብለው ሲያረዷት እጅግ በጣም ደነገጠች።😥

✍️የለበስኩት ጀለቢያ ነው ብርዱ የሌለ ነው ይባስ ብሎ ደብረሲናን እንዳለፍን መንገድ ተበላሽቶ ለ5ሰዓታት ያክል ቆምን።ብርዱ አጥንቴ ሲደርስ ይታወቀኛል። እንደምንም ሰንዳፋ ነው መሰለኝ ሹፌሩ ሶላት እንስገድ ብሎ ካቴናው ተፈታልኝና ውረድ ተባልኩ
😥ግን ሰውነቴ በረድ ሆኗልና አልታዘዘኝ አለ እግሬ ደርቋል መዘርጋት አልቻልኩም። ይህንን ሲያይ ሹፌሩ በጣም አዘነና እቅፍ አድርጎ አወረደኝና ትከሻውን ይዠ ሰውነቴን እንዳፍታታ አገዘኝ። አገር ስንጠያየቅ የአንድ ወረዳ ልጆች ሆንና በጣም ተሰማው በጣም ጀግና ኮማንደር ሹፌር ነበር።
✍️ዝሁርንና አስርን ሰግደን የማላውቃት አዲስአበባ ገባን። ይቀጥላል 😂

ወርቃማ ንግግሮች

19 Nov, 17:19


☔️ወደሗላ

✍️ከተማ ላይ የታየው እኔን አንድ ፍሬ ልጅ ለመያዝና ቤት ፍተሻው የትዕንቱን አስፈሪነት ሕብረተሰቡ ትልቅ ጭንቀት ስለፈጠረበት
፨ወላጆች ልጆቻቸው ጋ እየደወሉ ከቤት እንዳትወጡ ከተማ ረብሻ አለ በማለት ቀጭን ትእዛዝ አስተላልፈዋል። እኔኮ ያኔ 64ኪሎ ነው ብሆን ብዙም አረብሽም አልከብድምም ነበር😂😂

✍️ሰኞ ሕዳር 8/2012 ስራ ቦታ ከያዙኝና ቤት ፍተሻው ተጠናቆ በይነል መግሪብ ወል ኢሻእ በሆነ ወቅት"حسبي الله ونعم الوكيل" እያልኩ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ይዘውኝ ገቡና ከፌደራል ፓሊስ ለኮቻ ከተማ ፓሊስ ጣቢያ የአደራ እስረኛ ተብዬ ወደ እስረኛ ክፍል አስገብተው በሩን ከረቸሙብኝ። አንዳንድ ደፋር ሰዎች መጥተው ራት አምጥተንለታል ፍራሽም ይግባለት ብለው ሞገቱ በእርግጥ ፖሊስ ጣቢያው ያሉ ፖሊሶች ብዙወቹ ያውቁኛልና ደግሞ እሱ ምን አጠፋህ ተብሎ ነው ምናምን ብለው ለእኔ ለመወገን ሞከሩ።
✍️በስንት ጭቅጭቅ ራት እና ፍራሽ ወዘተ ገባልኝ ክላሱ ጨለማ ነው እኔም ንደት ብስጭት እየጀማመረኝ መጣ ክላሷ ውስጥ ያለው አንድ ሌላ ታሳሪ አብሽር ብሎ ሊያረጋጋኝ ሞከረ።

✍️በሩ ተከርችሞ ተቆልፏል።መብራቷ ቢልጭ ነው የምትለው በዚህ ሓል ማን ራት ይበላል ብዬ ሶላቴን ሰግጀ ለመተኛት ሞከርኩ። ልክ ለይል 7ሰዓት የተጣሉ ሰከራm እስረኞች መጡና በቃ በጣም እረበሹ ለእኔ የመጣውን ራት አገኙና ጥርግ አድርገው ከበሉ በሗላ ሰላም እንቅልፍ ተኙ።

✍️ለይሉ ነጋና ቀኑ ማክሰኞ ሆነ በሩ ተከፈተና እዛችው ጠባቧ ግቢ እግሬን ማፍታታት ጀመርኩ ። ማታውኑ ወንድማችን ፉላን ታስረ ወዘተ የሚል ኸበር በfb የከተማዋ ሙስሊሞች ፔጅ ተለቆ ስለነበር ሙሉ ሰው ሰምቷል። አስፈሪ ነው የተያዘው እንድህ እንድህ ነው የሚል ወሬ ስለተሰራጨ የሚቀርቡኝ አብረውኝ የሚውሉት ሳይቀር ጣቢያ መጥተው ለመጠየቅ ተቸግረው ነበር። አንዳንድ ደፋር ወንድሞችና እህቶች ቁርስ ይዘው መጡ እንዴት አደርክ ሲሉኝ አይኔ ፈጦ ነው ያደረው አልኳቸው😂 ሁሏንም ለመፃፍ ይከብዳል

✍️ማክሰኞ ረፋዱ 3ሰዓት አካባቢ አንድ መልከመልካም ጀመዓ ላይ የማውቀው ከመስጅድ የማይጠፋ ፖሊስ ካቴና ይዞ ወደ እኔ መጣና ወንድሜ ትእዛዝ ነው ይቅርታ አድርግልኝ በማለት ለመጀመሪያ ጊዜ እጄ በካቴና ተጠረነፈ። ወደየት ልትወስዱኝ ነው ስለው የስራ ቦታው ይፈተሽ ተብሏል አለኝና ከጣቢያው ይዞኝ ወጥቶ ፓትሮል ላይ ተጭኘ ዳይ ወደ መሓል ከተማ ስራ ቦታ አላህ አላህ
የስራ ቦታ ደረስንና ተከፍቶ ፈታተሹ ምንም ነገር የለምና ማታ ነበር ይህንንም መፈተሽ የነበረብን ልጁ እጁ ረጅም ነው አዳር አሸሽቶት ነው በማለት በንዴት ዐይን እርስበርስ ተያዩ።

✍️የስራ ቦታ አካባቢ ሰው የሱቁን በር ገርበብ አድርገው ይመለከታሉ እኔም በካቴና የታሰረውን ሁለቱንም እጄን ከፍ አድርጌ አሰላሙ ዐለይኩም አብሽሩ ደህና ነኝ ስል ሁሉም ከሱቁ ብቅ ብቅ የማለቱን ድፍረት አገኙና አብሽር አይዞህ አሉኝ።

✍️ታዳ የስራ ቦታ ተፈትሾ ከወጣን በሗላ ፓትሮላ ላይ ሆኘ አንድ ትራፊክ ጠጋ አለና ሸሁ ደግሞ ምን አጥፍተው ነው
በዚህ የለውጥ ጊዜ ደግሞ የሚረብሽ አለዴ በማለት ነገር ለማቀሳሰር ሞከር እኔም ገለማመጥኩትና ወደጣቢያችን አመራን።
✍️ጣቢያ ስደርስ ግቢው በሰው ተሞልቷል የጓደኞቸ እናቶች እህቶች እረ በቃ ጥልቅልቅ ብሏል ሐዘን ቤት መስሏል ግቢው እረ የሰው ሆድ ማባባት ብዬ ራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩ።

✍️ማክሰኞ እዛው ጣቢያ ዋልኩ አደርኩ እሮብም እንድሁ ከዘያሪዎቸ ጋ አሳለፍኩት።

✍️ሐሙስ ፌደራል ከመራያቸው ጋ መጡና ልብስ አምጡለት በሻንጣ ፌደራል ልንወስደው ነው አሉ ግን ወረቀት አልያዙም ነበር።ይቀጥላል

ወርቃማ ንግግሮች

19 Nov, 17:19


✍️ሰዎች ምንድን ነው ለማለት ለመጠየቅ መድፈር ተሳናቸው ድባቡ ትንሽ ያስፈራ ነበርና።ነሷራ አምናያዎቹ እሳት የሆነ ግልምጫቸውን መወርወር ጀመሩ እኔም ሓስቢየላህ ወኒዕመል ወኪል እያልኩ ራሴን ለማረጋጋት ሞከርኩ። አሁንም ባለሱፉ ከፌደራሎቹ ጋ ጠጋ ብሎ እንደማስጨነቅ አይነት መንገድ ተጠቅሞ ወደ ቤትህ ምራ በማለት ሲያንባርቅብኝ እኔም ኮስተር ብዬ ቤት የለኝም አልኩኝ
ሃሃሃሃ ቤት የለህም ጎዳና ነው ወይስ ጫካ የምት ኖረው በማለት አሾፉና ያችን ጥቁር ዱላ አስተካከሉ
✍️ኣሃ ሊወግሩኝ ነዋ ብዬ ተመትቸም ቤትም መርቸ ኣይይ ይሄማ አይሆንም ወዳጆቹ እንዲያዝኑ ጠላቶቸ ደስ እንድላቸው አላደርግም ብዬ ከውስጤ ጋ ተስማማሁና ወደ ቤት መምራቱን መረጥኩ ምክናያቱም ተመትቸም ቤትም በግድ መምራቴ አይቀርምና።

✍️ና ብለው ገፍተር ለማድረግ እየሞከሩ ፓትሮል ላይ ጫኑኝና በሒወቴ ጠባሳው የማይለቀኝን ስራ ሊሰሩ ወደ ሰፈር ቤት ፍተሻ ጉዞ ጀመርን።
✍️አንድ ባለሐብት ወንድም ስቴሽነሪ ሱቅ ላይ ተቀጥሬ እሰራ ስለነበር ከተማሪ እስከ የመንግስት ሰራተኛው በርካታው የከተማ ሕዝብ ያውቁኛልና በፓትሮል ተጭኘ ባዩ ጊዜ በድንጋጤ ራሱን የያዘ የሚያለቅስም መንገድ ዳር ቆሞ ሁኔታውንም የሚመለከት ሰው ሞልቷል።

✍️ፓትሮሉ ሰፈር በደረሰ ጊዜ የወታደሩን ድባብ ያዩ የሰፈር ሰወች ህፃናቶች ዋይታቸውን ለቀቁት።
፨ውሓ እየረጨሁ የማጫውታቸው በዚህ ጨዋታ ሱስ የሆነባቸው ከስራ ወደሰፈር መምጣቴን የሚጠባበቁት ህፃናቶች በዛች ቀን ግን ጨለማ የሆነባቸው መሳሪያ የደቀኑና የሰፈሩን ዋና ቦታዎች አቀባብለው በሚጠባበቁ ወታደሮች ተከብቤ ባዩኝ ጊዜ
😥ሰው የሚታሰረው ሰው ጋ ተጣልቶ መሆኑን ብቻ እሱኮ አይጣላም በማለት ከወላጆቻቸው ጋ ይዳረቃሉ።

✍️በዚህ መልኩ ግቢውን አቀባብለው የሚጠብቁ ወታደሮች ተመድበው የተወሰኑት እኔን ይዘው ወደ ቤት ውስጥ ገባን።
✍️እንደ እኔ ቤት ፍተሻ የሚባል ነገር በጣም አሳማሚ ከሕሊና የማይጠፋ ድርጊት ነው።

✍️ኪታቤን ከወጥ ጋ እያዳፉ ዘግናኙ የቤት ፍተሻ ተጀመረ ልብስን በጫማ እየረገጡና ውሓውንም እየደፉ ያጣድፉኝ ጀመር።
✍️አንዱ ፓስፓርት አገኘሁ ሲል ሌላኛው የስላቅ እየሳቀ ሶማሊያ ነው ሶሪያ የምትሄደው ይላል።
✍️ሌላው ፍላሾች አገኘሁ ሲል ኮርስ የሚሰጥበት ነው ይባባላሉ።የባንክ ደብተር አገኘሁ ሲለው ከአረብ አገር የሚቀበልበት ነዋ ይባባላሉ።

✍️ይሄ ሁሉ ኪታብ ምንድን ነው በማለት ከጫፍ ሲነካው ከመደርደሪያ ሙሉ ወረደ በጫማው ረገጠው እኔ ግን አሁን ደንዝዣለሁ

✍️ሰዓቱ እየመሸ ነው መግሪብ ደረሰ ያገኙትን ይዘው ከቤት ወጡና መሳሪያ አለህ አውጣ በማለት ያፋጥጡኝ ጀመር።እኔም እረ የለኝም አልኩ አንዱ ደብተራ አምንያ ማተቡን በእጁ ይዞ አንተ እኛን ልትገድል ነው በማለት በጥፊ ሊማታ ሲንደረደር አንድ ፌደራልና ፖሊስ እረፍ በሕግ ጥላ ስር ነው በማለት አስቆሙልኝ።
መሳሪያውን አውጣ እያሉ የተወሰነ ካስጨነቁኝ በሗላ ቀጥታ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ፓትሮል ላይ ጭነው ይዘውኝ ሄዱ።

✍️የመጀመሪያዋ የእስርቤት አዳር ......

ወርቃማ ንግግሮች

17 Nov, 16:00


☔️ወደ ሗላ ህዳር 8/3/2012 እና እኔ☔️

✍️ቀኑ ሰኞ ነው እንደ አገራችን ሳምንታዊ ቀን አቆጣጠር ሰኞ የመጀመሪያ ቀን የስራ ቀን ነው። እኔም ከሷሒቤ ጋ ከጀመርናት ስራ ላይ ተጥጃለሁ ነገር ግን ብዙ ጊዜ የማያቸው ሕልሞች ውለው ሳያድሩ በዟሒሩ ከች ይላሉና ጁሙዓ ለቅዳሜ ለይል አንድ ሕልም አይቸ ስለነበር በስጋትና በተበታተነ ሐሳብ ውስጥ ነኝ።ለሷሒቤ ሕልሜን ስለነገርኩት እሱም ስጋት ይዞታል ነገር ግን ያ ቀን ሰኞ ድባቡ ደስ ይላል ዝሁር ድረስ ቆየንና ወደየሰፈራችን አመራን።ምሳ በልተን ድጋሜ ወደ ስራ ገብተን ተፍ ተፍ ማለትን ጀመርን አስር ሶላት ደረሰና ሰግጀ ልቤ ጥሩ ስሜት ሲያጣብኝ ወደ እናቴ ደወልኩና ዘለግ ያለ ወሬ አወራ ምነው ድምፅህ አሞሓል እንዴ አለች እናቴ እኔም እረ ደህና ነኝ አልኩ ግራ በተጋባ ስሜት ከዛም በቃ ሰላም አምሹ ተባብለን ስልኩ ተዘጋ።
✍️ከ10ሰዓት ከ30በሗላ ነው የመንግስት ሰራተኛው የሚወጣበት ተማሪውም ከትምህርት የሚለቀቅበት ወቅት ደርሷል ወደ ከተማ ጎራ ብለው አስቤዛ የሚያደርጉ ሰዎች ከተማዋ ላይ የሚርመሰመሱበት ሰዓት ነው።በዚህ ሰዓት ከተማዋ ጭንቅ ጥብብ ብሏታል ፌደራሎች ፣ፖሊሶች ፣ልዩ ሚሽን ፈፃሚ ፖሊሶች ወዘተ አባላት ከተማዋ ዋና ዋና ቦታቸውን ይዘዋል።ከምሰራበት ሕንፃ ፊትለፊት ያለው ሕንፃ ላይ ስናይፐሮች ቦታቸውን ይዘዋል የተሽከርካሪዎች ሐረካ ተቀንሷል ።እኔ ግን ስራ ቦታዬ ውስጥ ነኝና ውጭ ላይ ምን እየተካሄደ እንደሆነ አላወኩም።
✍️ሁኔታውን የሚያዩ ሰዎች ምን አይነት ባለስልጣን ከተማችን መጥቶ ነው ወይስ ምን ምን አይነት ፀጉረ ልውጥ ገብቶ ነው የሚል የስጋት ወሬ ጫጫታ ተያይዟል።

✍️በዚህ ጊዜ ክትትል ክፍሉና የተመረጡ ፌደራሎች ከአጋዥ GPs ጋ በመሆን ከባንክ ባወጡት ፎቶዬ ተመርተው ሱራው ተመሳስሎባቸው አንድ ወንድማችን ሱቅ ጋ በመድረስ ይይዙታል በእርግጥ GpS እሱ አይደለም እያላቸው ነበር እነርሱ ግን መረጋጋት አልቻሉምና
✍️ሱራውን እያሳዩ ይህ አንተ ነህ አሉት ወንድማችንን በድንጋጤ እየተንተባተበ እረ እኔ አይደለሁም ሲላቸው በጣም መደነገጡን እንደ አድቫንቴጅ ተጠቅመው እሽ ይህንን ባለፎቶ ታውቀዋለህ ሲሉት የደነገጠ ሰው ችግር ነውና አወ አውቀዋለሁ አለ።
✍️አወ አውቀዋለሁ ካልክ ጉዳዩ ሲልሲላ አለውና ምራ የሚል ጥያቄ ይከተላል። እናም የት ነው ምራ ሲሉት እሽ በማለት ቀጥታ ወደ እኔ ስራ ቦታ ይዟቸው መጣ።

✍️ልክ ፎቁን ወጥተው ሱቅ በር ላይ ሲደርሱ ወንድማችን ጣቱን ወደ እኔ በመቀሰር 👉ይህ ነው አላቸው። እኔም ምንድን ነው ሸይኽ ፉላን ስል እንባው አይኑን ሲሞላው ተመለከትኩ ኣሓ ያ እጄ በካቴና ውስጥ ሲገባ ያየሁት ሕልም ዛሬም ግልፅ ሆኖ መጣ ማለት ነው ብዬ የያዝኩትን ትልቅ የጨርቅ መቀስ ይዠ ቀጥ ብዬ ቆምኩ።

፨ከተማዋ ውስጥ አይቸው የማላውቀው ሱፉን ደቅ አድርጎ የለበሰ ሰው ወደ ፊት ቀደም ብሎ ፉላን ማለት አንተ ነህ አለኝ ስልኩ ላይ ያለውን ከባንክ የወጣ ፎቶ እያሳየኝ።
እኔን ይመስላል እስኪ ስልኩን አምጣው ብዬ ጠጋ እንደማለት ስል በቅፅበት ረጃጅሞቹ ፌደራሎች ከቀኝም ከግራም እጄን ጠምዘዝ በማድረግ ጠፍንገው ያዙኝና የያዝኩትን መቀስ ቀምተው አስቀመጡ።

✍️ሱቁ ውስጥ ጓደኞቸ ደንግጠው እንደ እንጨት ደርቀዋል እኔ ቀድሞ ኢሻራው ስለመጣ ብዙም አልደነገጥኩም።ያው እጅ ሰጠሁ ማለት ነው ብዬ ለራሴ ነገርኩና ፀጥ አልኩ።

✍️ከሕንፃው በፍጥነት ይዘውኝ ወረዱና የሆነች ቅያስ አለች ወደሷ ገለል አድርገው በከበባ አስቀመጡኝ።በመገናኛ የሚያወሩት ቀውጢ ሆኗል። ሰዎች እንዴ እሱን ለመያዝ ነው ይህ ሁሉ ጋጋታና ወታደር ደህናውን ልጅ ይላሉ......

~ ከአቡ ሃላል… ከፌስቡክ መንደር የተገለበጠ ነው።

ወርቃማ ንግግሮች

17 Nov, 12:24


አስቡት በቀን ክፍለ ጊዜ ውስጥ የሆነ የተገደበ ሰዐት ብቻ ነው ወደ አላህ መመለስ ሚቻለው ብንባል

ማለትም ለ ምሳሌ ከ ጥዋት 4:00 ሰዐት እስከ ዕኩለ ቀን 6 ሰዐት ድረስ ብቻ ነው ላጠፋቹት ለወነጀላቹት ወንጀል ተውበት ማድረግ የምትችሉት ከዛ በተቀረ ሰዐት ተውበት ማድረግ አትችሉም ብንባል ወንጀል ሰርተን ተመሳሳይ ሰዐት እስከሚደርስ ምን ያህል መጠበቅ እንዳለብን
በመሀል ምን እንደምንሆን አናውቅም ተፀፅተንም no ያቺን ሰዐት መድረስ አለብህ ማን ወንጀል ስራ አለህ የለም ተቀባይነት ብንባል ? አስቡት ምን ያህል ከባድ እንደሆነ

ጌታችን ግን አዛኝ ነው ለኛ
ባሮቼ በየትኛውም ሰዐት ተፀፀቱ በየትኛውም ጊዜ ተመለሱ ምድረበዳ ለይ ግመሉ ጠፍታበት ሊሞት ሲል ምግቡን ይዛለት ስትመጣ ከሚደሰተው ባርያ በላይ እኔ በናንተ ወደኔ መምጣት እደሰታለው ከሰማይ እስከምድር በሚሞላ ወንጀል ብትመጡኝ እና ብትፀፀቱ እኔ ከሰማይ እስከምድር በሚሞላ ምህረት እመጣቹዋለው ምን አይነት ጌታ ነው ?
እኛስ ምን አይነት ደረቅ ባሮች ነን ይህን ያህል 😥

አሁንም ይነግረናል ባርያዬ የ ስንዝር ያህል ብትቀርበኝ የክንድ ያህል እቀርበሀው የ ክንድ ያህል ብትቀርበኝ የ እርምጃ ሚያህል እቀርበሀለው እየተራመድክ ብትቀርበኝ በመሮጥ ያህል ፍጥነት እቀርበሀለው ......ምን ያህል የ ላቀ ነው ጌታችን ?
እኛስ ምን ያህል ደረቅ ባሮች ነን 😥

ስለ ጌታችን ማውራት ብንቀጥል አያበቃም የሱ ምህረት ዕዝነት ቃላት አይጨርሱትም የኛን ድርቅናስ ምን ይገልፀው ይሆን ?😥

ዉደደኝ ቅረበኝ የሚል ልዉደድህ ልቅረብህ የሚል ጌታን ጀርባ ሰጥቶ መኖር ልማርህ ያጠፋሀው ጥፋት ለኔ ምንም ነው አንድ እንባ ሁሉንም ያብሰዋል አንተ ብቻ ተመለስኩ በለኝ የሚል ጌታን ምን ይሆን መልሳችን ? 😥

ይህ ግን ሁሌም አይቆይም ሩሀችን ከነፍሳችን በወጣችበት ቅፅበት ነገሩ ይቀየራል እያንዳንዱዋ ከጌታችን ርቀን ያሳለፍነው ሰዐት መሪር ፀፀት ነው ሚሆንብን የቀብር ቅጣት ከ እሳት ቅጣት በላይ ይህን ፍቅር የሚለግሰንን ጌታ ሙሉ ለሙሉ እናጣዋለን 😥

ሰዎች ጊዜ አለን እንመለስ ተውውው ወላሂ ፀፀቱን አንችለውም ነገሩ ቀልድ የሚገባው አይደለም !!

ወርቃማ ንግግሮች

17 Nov, 01:22


~ የንግሥና ባለቤት የሆይከው ጌታዮ ሆይ ፣ ፍላጎቶቼን ለአንተ ሰጥቻችኋለሁ ፣ ጥሩ ከሆነ አሳካልኝ መጥፎ ከሆነ በጥሩ ቀይርልኝ።


ውሎዮን ከአንተ መስመር ያልወጣሁ ሆኜ አውለኝ ፣ በሥራዬም የሕይወትን በሮች የሚከፍትልኝን ብስራት አብሥረኝ ፣…

ይህን ዱዓ በማለት ቀንህን ጀምር። የደስታ በሮች ለልባችሁ ..

~ እንደምን አደራችሁ
~ ሰብሃል ከይር

https://whatsapp.com/channel/0029VawofIrJP20yVRgdBb0D

ወርቃማ ንግግሮች

17 Nov, 01:08


በዋትስ አፕ ቻናል ከፍተናል ተጎራበቱን!!!

https://whatsapp.com/channel/0029VawofIrJP20yVRgdBb0D

ወርቃማ ንግግሮች

15 Nov, 09:40


አንዳንዱ ነገር በኛ ልፋት ብቻ አይወሰንምና ጀሊሉን መለመን ቀደሩን መቀበል ግድ ነው።

ልጅህ ጠማማ ቢሆን ያሳዝናል። እስከለፋህ ድረስ በልጁ ሁኔታ ራስህን አትውቀስ። ነብይ አሳድጎት የሚከፍ*"ርም ልጅ አለ።

ልጆችህ ባይስማሙ ቀልብ ይሰብራል። አንዱ ባንዱ ሲነሳ ያሳዝናል። ሆኖም ራስህን አዛ አታድርግ። ነቢላህ የእቁብ (አሰ) ያሳደጋቸው ልጆች በዩሱፍ ላይ ያደረጉትን አትርሳ።

ሚስቴ ጥሩ ባህሪ ለምን የላትም ብለህ አትገረም። የጠናው ቀደር የገጠመ እለት እንደ ሉጥ (አሰ) ሚስትህ በአመጸኞች ባህሪ ስር አድራ አላህ ካጠፋቸው ሰዎች ትሆናለች።

ባሌ ሀይለኛ ነው አመጸኛ ሆነ ብለሽ ራስሽን አትጉጂ። እስከሆነ ትኖሪያለሽ። ጀሊሉ በሂክማው አስያን በፊርአውን ስር ያሳቀፈ ጌታ ነው። እንደው በደፈናው አግራው እያሉ መኖር ነው።

ሰርቼ ለፍቼ ለምን ሀብታም አልሆንኩም ተብሎ ማማረር አያስፈልግም። መስራቱ እንጂ ሀብታም መሆን እጣህ ላይሆን ይችላል። እንደው የተሳሳተ ትርጓሜ እንጂ ለፍቶ ከሚኖር በላይ ሀብታም ማን አለ?

አላህ በቸርነቱ ዚክርን ተውባን ሰለዋትን ሀምድን ለሁሉም አድሏል። ያለከልካይ የፈለገ ከገኒማው እንዲዝቅ እና በሰኪና ባህር በዚህች አለም እንዲነግስባት ለሁሉም አድሏል። የኖሩት እንደነገሩን በዚህ ባብ ሲኖር ታዲያ ከ physical dimension ወጣ ብለው በሌላ ደረጃ ይኖራሉ። ከዛም ኢማን ይጣፍጣቸዋል።

ኢማን ስኳር ስኳር ወይም ማርማር አይልም። የራሱ ኢማን ኢማን የሚል ጣእም አለው። ረሱል እንዳሉት " 3 ነገሮችን በውስጡ የተገኘበት ሰው የኢማንን ሀላዋ ጣእም ቀምሷል አሉ 1) አላህና መልክተኛው ከነሱ ውጭ ካለ ሁሉ ይበልጥ የወደደ 2) ሰውን ሲወድ ምክንያቱ ለአላህ ብቻ ከሆነ 3) ወደ ኩፍ*ር መመለስን እሳት ላይ ከመጣል እኩል የሚጠላ ከሆነ።

መልካም ጁምአ

☞ Kha Abate 👦

ወርቃማ ንግግሮች

13 Nov, 17:14


ሳኡዲ ያላችሁ ከስልካችሁ ወደ ኢትዮጵያ ካርድ ለቤተሰብ  ከመላክ ከዛዉ ቢገዙ ይሻላል። መላክ ግዴታ ከሆነባችሁ ግን ባላችሁበት ሆናችሁ
➡️ የሳኡዲ ሰዋ ካርድ ባለ 23 ብልኩ
የኢትዮጵያ የ 400 ብር ካርድ
➡️ ባለ 20 ከላካችሁ የ 350 ብር ካርድ  የቤተሰብዎ ቁጥር ላይ በቀጥታ እናስገባለን! ወይም የኢትዮጵያን ካርድ በፎቶ እናስረክባለን እነሱ ቀጥታ እንዲደዉሉላችሁ ደዉለን እናሳዉቃለን
መገኛችን_✍️✍️⤵️
➽ቀጥታ ,ዋትሳብ ,ኢሞ እንዲሁም ቴሌግራም
   ➼ 05 06 32 50 65 ሳቢረት ሰኢድ 📞
መለያችን ፍጥነታችን


☞በቴሌግራም :- @Sabi2425

ወርቃማ ንግግሮች

13 Nov, 04:25


ይህ ቻናል በሀገር ውስጥ ያሉ ስራ አጥ
            ወንድም እህቶች
በአላህ ፍቃድ  የስራ ማግኛ ሰበብይሆን ዘንድ
ታስቦ የተከፈተና የስራ ማስታወቂያ የምንለቅበት
አዲስ ⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️ ነው 

🔗ተቀላቀሉ
t.me/+xN5NLvItoepjYjc0
t.me/+xN5NLvItoepjYjc0

ወርቃማ ንግግሮች

12 Nov, 17:43


ሚስትህን
ብቻችሁን ስትሆኑ ውቀሳት
በቤተሰቦችህ ፊት አመስግናት
በልጆችህ ፊት አሞግሳት
ስታገባ ግን ደብቀህ አግባባት😊

(መንቁል)

ወርቃማ ንግግሮች

08 Nov, 21:40


📍በቀን ክፈለ ጊዜ ላይ የሚተኙ ሶስት የእንቅልፍ አይነቶች አሉ እነሱም
(ሀይሉላ ፣ ቀይሉላ እና ዐይሉላ) ይባላሉ።

1 ሀይሉላ / حيلولة
ጠዋት ከፈጅር ቦሃላ የሚተኛ እንቅልፍ ነዉ ።
الحيلولة : هي النوم بعد صلاة الفجر وهي تحول بينك وبين رزقك.
📌 በሰዉዬዉ እና በርዝቁ መሀል መጋረጃ/ግርዶሽ ትሆናለች ፣ ዱኒያዊም ሆነ አኺራዊ ብዙ ማግኘት እና ማትረፍ የሚችል ነገር ታስመልጠዋለች ።
📌ነብያችን (ሰለላሁ አለይሂወሰለም) አላህ ለህዝባቸዉ የጠዋት ክፍለ ጊዜ ዉስጥ በረካ እንዲያደርግላቸዉ ዱዓ አድርገዋል ፣ ሁሌ በዚህ ሰዓት የሚተኛ ሰዉ ይሄ ዱዓም እንዳመለጠዉ ነዉ።

2 ቀይሉላ / قيلولة
ከዱሃ ሶላት ቦሃላ ወይም ከ ዙህር ሶላት ቦሃላ ለተወሰነ ደቂቃ ጋደም የምትባል እንቅልፍ ናት።

القيلولة : هي النوم بعد صلاة الضحى او بعد صلاة الظهر لمدة 30 دقيقه وهي مفيدة للصحة الجسم للتقوية على العبادة.
📌ለአካል ጤና እጅግ በጣም ጣቃሚ ነዉ።
📌ኢባዳ ላይ ኢንዲያጠናክረዉ ነይቶ የተኛ ሰዉ አጅር ያገኝበታል ።
📌ሶሃባዎች እና በርካታ አኢማዎች ይተኟት ነበረ።

3 ዐይሉላ /عيلولة
ከ አሱር ሶላት ቦሃላ የሚተኛ እንቅልፍ ነዉ።
العيلولة: هي النوم بعد صلاة العصر وهي تسبب علة للجسم والنفس وضيق لصدر.
📌በዚህ ጊዜ መተኛት የተከለከለ መሆኑ እና እጅግ በጣም የጠላ መሆኑን በሰሂህ ሀዲስ ተዘግበዋል ፣ የሚያስተኛዉ በቂ የሆነ ምክንያት/ዑዝር ከሌለዉ በቀር ።
📌በጤናችንም ላይ ለበሽታ ሰዉን ያጋልጣል
📌ለጭንቀት እና የሀሳብ ጥበት ላይ ሰዉን ይጥላል።


እናንተስ በዬትኛዉ ሰዐት ላይ የመተኛት ልምድ ነዉ ያላችሁ? ምን ምንስ ታዝባቹሃል?

ወርቃማ ንግግሮች

08 Nov, 21:36


ልዩ ኸበር - የጥንቱን ፍለጋ፡ ከአንደሉስ እስከ መካ

ከሠላሳ አራት ዓመታት በፊት ነው - እ.አ.አ በ1990፡፡ ስፔናዊው ራፋኤል ፈርናንዴዝ ከእስልምና ጋር ተዋወቀ፡፡ መምሕሩና የጂኦግራፊ አጥኚው ሰው አላህ ልቡን ወደ እውነት ስለመራው ደስታው ወደር አልነበረውም፡፡ ደስታው በትኩሱ ሳለ ለጌታው የገባው ቃል እንዲህ የሚል ነበር - “ሐጅ የማደርገው በፈረስ ተጉዤ ነው”፡፡ ይህ ለወቅቱ ጉልበታም ወጣት በአንድ ጊዜ የሚቻል አልነበረም፡፡ ጉልበት ብቻ አይደለም፣ ጊዜ እና ገንዘብ የሚጠይቅ ቃል ኪዳን ነበር፡፡ ጉልበት፣ ጊዜ እና ገንዘብ ቢሟላም ጽናት የሚጠይቅም ነበር፡፡ ስለዚህ መታገስ ነበረበት፡፡

ከ35 ዓመታት በኋላ የዚያን ጊዜው ወጣት ራፋኤል ፈርናንዴዝ፤ በእስልምና ሥሙ ዓብደላህ ተብሎ የሚጠራ ሆኗል፡፡ አብዱላህ በዩኒቨርሲቲ ባጠናው ጂኦግራፊ፣ በዲግሪ ላይ ሌላ ዲግሪ እየደረበ የዶክትሬት ማዕረግ ላይ ደርሷል፡፡ በትምሕርት ረዥም ርቀት በመጓዝ ብቻ ሳይወሰን ወጣት ሳለ ቃል ኪዳን ገብቶ ያልፈጸመውን ሐጅን በፈረስ ጀርባ ተንጠላጥሎ ወደ ቅዱሳኑ ሥፍራዎች የመድረስ ውጥን ለማሟላት ዝግጁ ሆኗል፡፡

ዓብደላህ በዚህ መልኩ ለሐጅ ሥነ ሥርዐት ሲነሳ አርዓያ ያደረገው ከ500 ዓመታት በፊት በአንደሉስ ምድር የነበሩ በጀግንነት የሚያወድሳቸውን አያት ቅድመ አያቶቹን ነው፡፡ በርግጥ የፈረስ ግልቢያ መውደዱ፣ ከዚያም ሲያልፍ በአንዳንድ ውድድሮች ላይ ተሳትፎ ማሸነፉ ይህን መንገድ እንዲመርጥ አስችሎታል፡፡ በጉዞው አያት ቅድመ አያቶቹንም አብሮ ያስታውሳል፡፡ ዓብዱላህ የቅድመ አያቶች አንደሉስ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ሥፍራዋ ከፍ ያለ መሆኑንም ያውቃል፡፡ እነርሱ ያን ጊዜ የጌታን ትእዛዝ ለመሙላት ፀሐይ እና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው ሀገራትን አቋርጠው ከ8 ሺሕ ኪሎ ሜትር በኋላ ሳዑዲ ዐረቢያ እንደሚደርሱም ከድርሳናት አንብቧል፡፡

ዓብዱላህ ፌርናንዴዝ ያለፉት ዓመታት ይህን ገድል ለመድገም የተጋበት ነበር፡፡ የጉዞ እቅድ ነደፈ፣ ራሱን የፕሮጀክቱ ዋና አስተባባሪ በማድረግ ይህን ፅናት የሚጠይቅ ጉዞ በማድረግ በርትተው የሚያበረቱን ባልንጀሮች መፈለግ ጀመረና የሕልሙን ተጋሪዎች አገኘ፡፡ እነዚህ የሕልም ተጋሪዎቹ ሙሐመድ ሚስባሂ፣ እስማኢል ጎንዛሌዝ፣ ዑመር ከሪም፣ ሙጃሂድ ኤስፒኖ፣ ዑመር ሚላኒሮ እና ዓብዱልቃድር ሃርካሲ ሆኑ፡፡ ዓብዱላህ ሕልሙን የሚጋሩትን ሰዎች ከማግኘት ውጪ ሌሎች መሟላት የሚኖርባቸው ሎጂስቲክሶችን ለማግኘት እንቅስቃሴውን ቀጠለ፡፡ ሰዎቹን 8 ሺሕ ኪሎ ሜትር አቆራርጠው ሳዑዲ ዐረቢያ ምድር ላይ የሚያደርሱ ብርቱ ፈረሶችን መፈለግ ተጀመረ፡፡ የትኞቹ ዝርያዎች የተሻለ ብርታት፣ ቅልጥፍና እና ጉልበት አላቸው ብሎ መምረጥ ስለነበረበትም በማፈላለግ የዐረቢያ ዝርያ ያላቸው ፈረሶችን ለጉዞው ተስማሚ ሆኖ አገኛቸው፡፡ ፈረሶቹን ማሠልጠንና ምግባቸውን እየመረጡ ጡንቻቸው እንዲፈረጥም ማድረግ የእለት ተእለት ሥራው ሆነ፡፡ ብርታት የሚጨምሩ ተግባራት ሲደረጉ የነበሩት ለፈረሶቹ ብቻ ግን አልነበረም፡፡ የጉዞው ተሳታፊዎችም ይህንኑ ሲከውኑ ቆዩ፡፡ በዚህ ሒደት የሕክምና ባለሞያዎች የሚያስፈልገውን እገዛ እያደረጉ ቆይተዋል፡፡

ቀጣዩ ሒደት የነበረው የፈረሶቹን ጉልበት መለካት ነበር፡፡ እነ ዓብዱላህም ወደፊት የሚጠብቃቸውን ብርታት የሚጠይቅ ጉዞ የሚሞክሩበት ቀን ተቆረጠ፡፡ ለሙከራው የተመረጠው የሰሜናዊ ስፔን ክፍል ነበር፡፡ 2021 ክረምት የመጀመሪያው የፈረስ ጉዞ ተጀመረ፡፡ ዓብዱላህ እና የሕልም ተጋሪዎቹ ለአስራ ስድስት ቀናት ባደረጉት የፈረስ ላይ ጉዞ 700 ከሎ ሜትር መሸፈን ቻሉ፡፡ የፈረሱም የሰውም ጉልበት ተፈተሸ፡፡ ስለ ጉዞው እነ ዓብዱላህ ሲናገሩ “ፈታኝ ቢሆንም ስኬታማ ነበር” ይላሉ፡፡ ጉልበት ከሚፈትሸውና ከሌላው ሁሉ “ጠንካራ ወዳጅነት እንዲኖረን አድርጎናል” ብለዋል፡፡ ይህ ሲጠናቀቅ ሌላ አንድ ዓመት ጠብቀው ሁለተኛው ጉዞ ማድረግ ነበረባቸው፤ አደረጉት፡፡ በአጎራባች ፖርቹጋል በኩል ከሰሜን ወደ ደቡብ የተደረገው የፈረስ ላይ ጉዞ በ2022 የተደረገ ነበር፡፡ ይህ ጉዞ እንደቀደመው ጊዜ 16 ቀናት ሲፈጅ፤ የሸፈኑት 600 ኪሎ ሜትር ነው፡፡ ይህ ቁጥር ቀድሞ ከተመዘገበው ያነሰ ነው፡፡ እነ ዓብዱላህ ለዚህ ሰበብ የሆነው የአየር ሁኔታው በጣም ደረቅ መሆኑ እንዲሁም “በማናውቀው ሀገር እና ቋንቋ ጉዞውን ማድረጋችን ነው” ሲል ያስታውሳሉ፡፡ ይህ ቢሆንም ለቀጣይ ጉዞ በርካታ ስንቅ የተያዘበት ነበር ይላል፡፡

አሁንም ይህ ብርታት የሚጠይቅ ልምምድ እንደቀጠለ ነው፡፡ ከወራት በፊት ከአንደሉስያ ምእራባዊ አካባቢ የተነሱት እነ ዓብዱላህ ወደ ምሥራቅ አቅጣጫ ከረር ባለ ፀሐይ ውስጥ ትግላቸውን ቀጥለዋል፡፡ ቀኑ ከረር ያለ ፀሐይ ቢያስተናግድም ሌሊቱ እጅግ በጣም ቀዝቃዛ የሚባል ስለነበር ከሁለቱ የልምምድ ጉዞዎች ለየት ያለ አጋጣሚ ማስተናገድ ግድ ሆኖባቸዋል፡፡ በዚህ የአየር ጠባይ 420 ኪሎ ሜትር ሸፍነው ተመለሱ፡፡ በተለይ በምሽት በደረሱበት እሳት እያቀጣጠሉ መሞቅ ግድ ነበር፡፡ በፈረስ ላይ ከአንደሉስ ምእራብ አቅጣጫ ወደ ምሥራቅ ተጉዘው ግራናዳ ሲደርሱ የተወሰኑ ሰዎች አቀባበል አደረጉላቸው፡፡

አሁን ልምምዱ አበቃ፡፡ የፈረስ ላይ የሐጅ ተጓዦቹ ቀድመው እቅድ ሲያወጡ አላህ ቢፈቅድ መድረስ የሚፈልጉት በዚህ ዓመት በሚከናወነው የሐጅ ሥነ ሥርዐት ነው፡፡ ሆኖም ከፊታቸው ስምንት ሺሕ ኪሎ ሜትር መጓዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ከደቡባዊ ስፔን ተነስተው፣ ዐስር ሀገራትን ያቆራርጣሉ፡፡ ፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ስሎቬንያ፣ ክሮሽያ፣ ቦስንያ፣ ሞንቴኔግሮ፣ ኮሶቮ፣ ሰሜን ሜቄዶንያ፣ ቡልጋሪያ፣ ቱርክ ደርሰው ቀይ ባህርን በጀልባ ተሳፍረው ግብጽ መድረስ ይኖርባቸዋል፡፡ ከግብጽ ደግሞ ቅዱሳኑን ሥፍራዎች ወደያዘችው ሳዑዲ ዐረቢያ መጓዝም አለ፡፡

ይህ 35 ዓመት ያስቆጠረን ቃል ኪዳን ለመሙላት የሚደረገው ጉዞ ከ23 ቀናት በፊት ተጀመረ፡፡ ዶክተር ዐብዱላህ ፌርናንዴዝ ዝግጅቱን ሲጀምሩ ከስድስት ሰዎች ጋር የነበረ ቢሆንም እንደ አለመታደል አሁን የጉዞው ተሳታፊዎች አራት ቀርተዋል፡፡ የእንስሳት ሐኪም፣ ነርስ፣ ምግብ አብሳይ እና ሌሎች ጉዳዮችን የሚያስፈጽሙ ሰዎችም በመኪና ይከተሏቸዋል፡፡ ሕልም የሚመስለው ለአላህ የተገባን ቃል ኪዳን የመሙላት ጉዞ እነ ዓብዱላህ ጥንት አያት ቅድመ አያታቻቸው እንዳደረጉት መነሻውን በአንደሉስ ውስጥ በሚገኘው አልሞናስቴር መስጂድ አድርጓል፡፡ ተጓዦቹ የእለቱ የት እንደደረሱ ኢንስታግራም እና ፌስቡክን በመሳሰሉ ማኅበራዊ ትስስር መድረኮች ያጋራሉ፡፡ እስከ ትላንት ሐሙሰ ድረስም 935 ኪሎ ሜትር መጓዝ የቻሉት እነ ዓብዱላህ፤ ቀሪ ከ7 ሺሕ በላይ ኪሎ ሜትሮችን ለቃል በመታመን እና ቅዱሳኑን ሥፍራዎች በመናፈቅ ቀጥለዋል፡፡ (ሚንበር ቲቪ)

በድረ ገጽ ያንብቡ፡- https://minbertv.com/?p=9384

ወርቃማ ንግግሮች

08 Nov, 20:55


~•

እውነትን የያዙ ሰዎች ሐሰተኞችን ከመቃወም ዝም ሲሉ ሐሰትን የያዙ ሰዎች በእውነት ላይ እንዳሉ ይሰማቸዋል።

[ዐሊ ኢብን አቢ ጣሊብ]

ወርቃማ ንግግሮች

05 Nov, 18:00


⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️ ባለቤቶች

የሱና ቻናል ተደራሽነት ይበልጥ ይሰፋ ዘንድ
የቻናል ሊንክ መላክ ትችላላችሁ  ⚡️

✍️መስፈርት 1/ :- የሱና ቻናል ሊሆን ስለማጣራ⚫️
✍️መስፈርት2/ ከ1k member በላይ 🔤 ከዛበታች
✍️መስፈርት 3/:-  ቻናሉን አይቼ አሳውቃቹኋለሁ

🚫ግሩፕ አልቀበልም

⭐️ @twhidfirst1
🌟 @twhidfirst1

ወርቃማ ንግግሮች

03 Nov, 18:37


🔤🔤🔤🔤🔠🔠🔠🔠🔤🔠

🔤 الأربعون النبوية في السعادة الزوجية

🎤ኡስታዝ ኢብራሂም ኸይረዲን

🌹
   
🌹
       
🌹
            
🌹
                
🌹
ገባ ገባ በሉ ባረከሏሁ ፊኩም ተከታተሉ


🔗🔡🔡🔡
https://t.me/tdarna_islam?livestream
https://t.me/tdarna_islam?livestream

ወርቃማ ንግግሮች

03 Nov, 14:21


አብዛኛዉ ሰዉ ቁርዓን እየቀራ ሱጁድ ያለበት አንቀፅ ላይ ሲደርስ በሱጁድ ላይ ምን እንደሚባል አያዉቅም።

ይሀዉላችሁ የሱጁድ ዱዓዉ/ ዝክሩ

اللهم لك سجدت و بك آمنت ولك أسلمت سجد وجهي للذي خلقه وصوره وشق سمعه وبصره تبارك الله أحسن الخالقين

አለሁማ ለከ ሰጀድቱ ወቢከ ዓመንቱ ወለካ አስለምቱ ፣ ሰጀደ ወጅሂ ሊለዚ ኸለቀሁ ወሰወረሁ ወሸቀ ሰምዐሁ ወበሰረሁ ፣ ተባረከላሁ አህሰነል ኻሊቂን።

👌ቢሸመደድ ይወደዳል።

ወርቃማ ንግግሮች

31 Oct, 14:25


~ ለመማርና ለማስተማር ይሆነኝ ዘንድ ቀለምን መረጥኩ። ከሀሳቦቼ መልካሙን ለማካፈል ብዬ ትንሽዬ ቤት ሰራሁ።

https://t.me/thetravelersoul

ቤትህ( ቻናልህ)  ላይ ማስታወቂያ ይፈቀድ ከሆነ እንግዶችን ትጋብዝልኝ ይሆን ወንድሜዋ?

ወርቃማ ንግግሮች

31 Oct, 02:27


ደስ የሚለው የአኺራ ጉዞ ላይ የቀደመ የውድቀት ታሪክህ መጪውን ስኬት አይወስንም። ዛሬ አንድ ብለህ መጀመር ትችላለህ!
የፊርዐውን ድግምተኞች ምስክር ናቸው። "በሙሳ እና በሃሩን ጌታ አመንን" ባሉ ጊዜ የልቅና በር ወዲያው ተከፈተላቸው! የተዋረዱት ድግምተኞች ታላላቅ ወልዮች ሆኑ!
#በተውበት
#በኒያ
#በትጋት
ነገህ የተሻለ እንደሚሆን አትጠራጠር👌

ወርቃማ ንግግሮች

28 Oct, 17:43


   📖🌙🌙

🌹🌹🌹
         🌹🌹🌹🌹        👈አበባውን🔻
      🌹🌹🌹🌹🌹            በመንካት 🔻
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹           ጠቃሚ 🔻
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹       ነገር ያግኙ🎁
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹         🔻
      🌹🌹🌹🌹🌹             🔻
         🌿🌹🌹🌿       🔻
              🌿🌿            🔻
                 🌿                     🌿🔻
                  🌿               🌿🌿🔻
                 🌿           🌿🌿🌿🔻
                🌿      🌿🌿🌿🌿🔻
               🌿    🌿🌿🌿🌿🔻
              🌿 🌿🌿🌿🌿🔻
               🌿 🌿🌿🌿🔻
                 🌿              .🔻
                  🌿               .🔻
                   🌿                  .🔻
                    🌿                    .🔻
                    🌿
                  🌿       🌿

⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️📡💡🌙

ወርቃማ ንግግሮች

26 Oct, 19:11


ኑዛዜዬ ይህ ነው…! እስከሕይወቴ መጨረሻ የታመንኩለትን የፍልስጤም ውዴታ፣ በጫንቃዎቼ የተሸከምኩትን ታላቅ ሕልም ከዳር አድርሱ። እኔ ብወድቅ እናንተ አትውደቁ። ወደመሬት ያልጣልኩትን ሠንደቅ ዓላማ ከፍ አድርጋችሁ አውለውልቡ። መስዋዕትነቴን እንደድልድይ ተጠቅማችሁ ለተተኪው ክንደ ብርቱ ትውልድ መደላድሉን ፍጠሩ። እናት አገር በተግባር የሚኖሩት ተጨባጭ እንጂ የሚተርኩት ተረክ አይደለምና በሚሰዋው እያንዳንዱ ታጋይ እልፍ ተተኪዎች እንደሚፈጠሩ ጥርጣሬ አይግባችሁ።

የእኔ ተራ ደርሶ ከተለየኋችሁ የነፃነቱ ማዕበል የመጀመሪያ ጠብታ እንደነበርኩ፣ ሕይወቴንም ጉዟችሁን ስትፈጽሙ በማየት ጉጉት የገፋሁ መሆኔን አትዘንጉ። በጠላታችሁ ጉሮሮ ውስጥ የተሰካችሁ እሾህ ሁኑ። ዓለም ለሐቃችን መታገላችንን እስኪረዳ፣ ለዕለታዊ ዜና የቁጥር ግብዓት ብቻ እንዳልሆንን እስኪገነዘብ ድረስ ትግላችሁን ቀጥሉ።

የሕያ ኢብራሂም ሲንዋር | ጋዛ
----------

ወርቃማ ንግግሮች

26 Oct, 19:11


*ታሪካዊው የሸሂድ የሕያ ሲንዋር ኑዛዜ*

አቡ ሊና የተባለ ድንቅ ብዕረኛ፣ በኻን ዩኒስ የዘካ ኮሚሽን ፕሬዚደንት ዶ/ር ጀሚል አቡ ቢላል ይፋ የተደረገውን የሸሂድ የህያ ሲንዋር ኑዛዜ፣ "የጋዛው ሸሂድ የሕያ ሲንዋር ኑዛዜ" በሚል ርዕስ በጣም ግሩም በኾነ የቋንቋ ጥራት ወደ አማርኛ መልሶት በሳምንታዊው አዲስ አድማስ ጋዜጣ የዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 16፣ 2017 እትም ላይ አስነብቦናል።

የሸሂድ የሕያ ኑዛዜ እጅግ በጣም መሳጭ እና በፍሬም ተደርጎ ለታሪክ የሚቀመጥ የእውነተኛ ታጋይ ውብ ቃል ነው።
የሸሂድ የሕያ ኑዛዜ እጅግ ብዙ መስዋዕትነት እያስከፈለ የሚገኘው የፍልስጥኤማውያን የነጻነት ትግል የሚካሄድበትን ከብረት የጠነከሩ መንፈስ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ፣ ብዙ ሺህ የሕያ ሲንዋሮችን የሚወልድ፣ ትውልዶች የሚቀባበሉት የትግል ቃል-ኪዳን ችቦ ኾኖ ሲያበራ እንደሚኖር መጠራጠር የሚቻል አይመስኝም።

አቡ ሊና በሚሰኝ የብዕር ስም የሸሂድ የሕያ ሲንዋርን ኑዛዜ በሚጣፍጥ አማርኛ ተርጉሞ ላስነበበን ወንድም ልባዊ አድናቆቴንና የከበረ ምሥጋናዬን ለማቅረብ እወድዳለሁ።

--------

▪️ የጋዛው ሸሂድ የሕያ ሲንዋር ኑዛዜ!
➤ [የኻን ዩኑስ የዘካ ኮሚሽን ፕሬዚደንት ዶ/ር ጀሚል አቡ ቢላል እንዳስተላለፉት ]
———

እኔ ግዞትን ወደጊዜያዊ እናት አገር፣ ሕልሙንም ወደዳርቻ የለሽ ትግል መለወጥ የቻለ ስደተኛ ልጅ የሕያ (ሲንዋር) ነኝ። እኒህን ቃላት ስደረድር የሕይወቴን ቅፅበቶች በመላ እያስታወስኩ ነው። ያደግኩባቸውን ጠባብ ጎዳናዎች፣ ያሳለፍኩትን ረጅም የወህኒ ኑሮ፣ በፍልስጤም ምድር የፈሰሰችዋን እያንዳንዷን ደም አስታውሳለሁ።

ፍልስጤም አንዲት ቅዳጅ ትውስታ፣ በፖለቲከኞች ጠረጴዛ ላይ የተረሳች ቁራጭ ካርታ በሆነችበት ዘመን በኻን ዩኑስ የስደተኞች መጠለያ በ1962 ተወለድኩ። ሕይወቴ የተፈተለው በእሳት እና አመድ መካከል ነበር። በወረራ ሥር መኖር ዘላለማዊ ወህኒ መሆኑን ገና በልጅ ዕድሜዬ ተረዳሁ። በፍልስጤም ምድር ተርታ የሚባል ሕይወት እንደሌለ በአፍላነቴ ተገነዘብኩ። በዚህች ምድር እኖራለሁ ያለ ሰው ዝናሩ የማይነጥፍ መሣሪያ በልቦናው ይታጠቅ፣ ለረጅሙ የነፃነት ጉዞ መንፈሱን ያዘጋጅ ዘንድ ግድ ይለዋል።

ኑዛዜዬ ከዚህ ይጀምራል…! ወረራውን በመቃወም የመጀመሪያዋን ድንጋይ ከወረወረው ታዳጊ ግዙፍ እውነታን ተረድተናል። የምንወረውራት እያንዳንዷ ድንጋይ ቁስላችንን አይቶ ዝም ላለው ዓለም የምናሰማት ቃላችን ናት። የሰው ማንነት የሚለካው በዕድሜው ሳይሆን ለእናት አገሩ በከፈለው መስዋዕትነት መሆኑን የጋዛ ጎዳናዎች አስተምረውኛል። የእኔም ሕይወት ያለፈው በዚሁ መልክ ነበር… ተደጋጋሚ ወህኒ፣ በርካታ ውጊያ፣ የበዛ ሕመም እና እስከገደፉ በተስፋ የተሞላ ሙቅ ሕይወት…

በ1988 ነበር የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶብኝ ለመጀመሪያ ጊዜ ወህኒ ቤት የገባሁት። ፍርኃትን ከነጭራሹ አላውቀውም። በጨለማ የእስር ቤት ክፍሎች ሆኜም በግድግዳው ገጽ ላይ ወደሰፊው አድማስ የሚከፈት መስኮት፣ በብረት ፍርግርጎቹ መካከልም የነፃነቱን ጉዞ የሚያበራ ፋኖስ ይታየኝ ነበር። በእስር ቤት ሶብር መልካም ባህሪ ብቻ አለመሆኑን፣ ይልቁንም ባህርን ጠብታ በጠብታ የመጭለፍ ያክል እንደብረት ጠንካራ መሣሪያ መሆኑን ተረዳሁ።

ኑዛዜዬን እንካችሁ…! ወህኒ ቤትን አትፍሩ። ወህኒ ቤት የነፃነት ጉዟችን አንድ ግብዓት ነው። ነፃነት ከተሰረቀ መብት ይልቅ ከህመም ተፀንሶ በትዕግስት የሚቀረጽ ሐሳብ መሆኑን የተማርኩበት መድረሳ ነው።

በ2011 በ"ወፋኡል አሕራር" የእስረኛ ልውውጥ ስምምነት ስፈታ ማንነቴ እጅጉን መቀየሩን ለማስተዋል በቃሁ። የወጣሁት እምነቴ ጠንክሮ ነበር። ትግላችንም ከትግልነት ባለፈ እስከ መጨረሻዋ የደም እንጥፍጣፌያችን ተሸክመነው የምንዘልቅ የአላህ ውሳኔ (ቀደር) መሆኑን ተገንዝቤ ነበር።

ኑዛዜዬን እንካችሁ…! ነፍጣችሁን፣ ለድርድር የማይቀርብ ክብራችሁን፣ መሞት የማያውቅ ሕልማችሁን አጥብቃችሁ ያዙ። ጠላት ትግላችንን ማስቆም ይሻል። ወኔያችንን በማለቂያ የለሽ የድርድር ተስፋ ጠፍሮ ለማኮላሸት ይደክማል። እኔ ግን እላችኋለሁ… በመብታችሁ አትደራደሩ። ትግላችን በተሸከምነው ነፍጥ ብቻ የሚሰፈር አለመሆኑን አትርሱ። ትግላችን ፍልስጤምን መውደዳችን፣ በከበባና በድብደባ የማይፈታ ወኔያችን መሆኑን አስታውሱ።

ኑዛዜዬን እንካችሁ…! ለሸሂዶቻችን ደም ታማኝ ሁኑ። እሾሃማውን መንገድ ያሳየን ትውልድ በደሙ መስዋዕትነት የነፃነትን መንገድ አስጀምሮናልና በፖለቲካ ጨዋታ፣ በዲፕሎማሲ ውስለታ ክብሩን ዝቅ ከማድረግ ተጠንቀቁ። የእኛ መኖር ዓላማ ቀደምቶቻችን የጀመሩትን ትግል ከዳር ማድረስ ነውና የፈለገው ቢሆን ከመንገድ ማፈንገጥ አይገባም። ጋዛ ምንጊዜም የትግሉ ዋና ከተማ፣ የፍልስጤማዊ ወኔ መቀመጫ ልቦና ሆና ኖራለች። ወደፊትም ትኖራለች።

በ2017 የሐማስን የጋዛ ክንፍ አመራር ኃላፊነት ስወስድ ለእኔ ጉዳዩ የአመራር መቀያየር ጉዳይ ብቻ አልነበረም። ይልቁንም ከወንጭፍ ጀምሮ ወደነፍጥ ያደገው ገናና ትግላችን ዕድሜ የቀጣይነት ሠንሠለት ነበር። በእያንዳንዷ ቀናት የሕዝባችንን ዘወትራዊ ፍዳ በዓይኔ በብረቱ ታዝቤያለሁ። የነፃነት ጉዟችን እያንዳንዷ እርምጃም ብዙ መስዋዕትነት የሚከፈልባት መሆኑን ተረድቻለሁ።

አንድ ነገር ግን እርግጠኛ ሆኜ እነግራችኋለሁ…! እጅ መስጠት የባሰ ዋጋ ያስከፍለናል። ግዴለም በጥንካሬያችን እንዝለቅ። ዛፍ በሥሮቹ አፈሩን አንቆ እንደሚረጋ ሁሉ የፍልስጤምን አፈር ሙጭጭ አድርገን እንያዝ። ለመኖር የወሰነን ሕዝብ የትኛውም ንፋስ ከመሬቱ ሊነቅለው ከቶ አይችልም።

የአቅሷ ማዕበል ዘመቻ መሪ መሆን ለእኔ ትልቅ ክብር ነበር። የአንድ ግሩፕ ወይም የአንድ ንቅናቄ መሪ ሳይሆን ነፃነትን የሚያልም ፍልስጤማዊ ሁሉ ድምጽ መሆን እንደቻልኩ ተሰምቶኛል። ትግል ኃላፊነት እንጂ ምርጫ እንዳልሆነ ሁሌም እረዳ ነበር። እናም ይህ ልዩ ዘመቻ በፍልስጤማውያን የትግል መዝገብ አዲስ ገጽ የሚገልጥ፣ የተለያዩ ታጋይ ቡድኖችን በጠላት ፊት በአንድነት የሚያሠልፍ ዘመቻ እንዲሆን ጥልቅ ፍላጎት ነበረኝ፤ ጠላታችን ሕፃን ከሽማግሌ፣ ድንጋይ ከዛፍ ሳይለይ ሁሉንም ያጠቃልና።

ኑዛዜዬ ግለሰባዊ አይደለም…! ይልቁንም ነፃነትን ለሚያልም እያንዳንዱ ፍልስጤማዊ ሁሉ፣ በትከሻዋ ሰማዕት ልጇን ለምትሸከም እናት ሁሉ፣ በዕኩያን ጥይት ልጁ ለተገደለችበት አባት ሁሉ የጋራ ስንቅ የሚሆን ውርስ ነው።

የመጨረሻ ኑዛዜዬን እንካችሁ…! ትግላችን መና እንደማይቀር አትርሱ። የምንከፍለውን ዋጋ ብቻ ሳይሆን በወኔ እና በክቡር ስብዕና ጌጠን የኖርነውን ሕይወት አስታውሱ። የጋዛ የከበባ ኑሮና የወህኒ ውጣ ውረድ ትግሉ ትከሻ የሚያጎብጥ፣ ጉዞውም ሰውነት የሚያዝል መሆኑን አስተምሮኛል። ግና እጅ አልሰጥም ባይ ሕዝብ ብዙ ተዓምር ይሠራል።

ከምድራዊ ሕይወት ፍትህ አትጠብቁ። የዓለም ሕዝብ ሕመማችንን ዓይቶ እንዳላየ መሆን መምረጡን ስረዳ ኖሬያለሁ። እናንተም መረዳታችሁ አይቀርምና ከሌሎች ፍትህ መጠበቁን ትታችሁ ራሳችሁ ፍትህ ሁኑ። የፍልስጤምን ሕልም በልቦናችሁ ያዙ። ከእያንዳንዱ ቁስለት ጥንካሬን፣ ከእያንዳንዷ ዘለላ እንባ ተስፋን መምዘዝ ተማሩ።

ይሃችሁ የእኔ ኑዛዜ ነው…! መሣሪያችሁን በፍጹም አትጣሉ። ወንጭፎቻችሁን አታስቀምጡ። ሸሂዶቻችሁን አትዘንጉ። ሕልማችሁን አትተዉ። እኛ በአፈራችን፣ በልቦናችን፣ በልጆቻችን የወደፊት ተስፋ ውስጥ እንደምንኖር አትዘንጉ።

ወርቃማ ንግግሮች

26 Oct, 18:20


ታሞበት ይዞ የመጣ ባለ ሚኒባስ ወንድም እኔ በነፃ ላድርስላችሁ ብሎ አደረሰልን፣ አስክሬኑንም በቤቱ አሳረፍን😭 😭😭

በዕለተ ማክሰኞ ጥቅምት 05/2017 ዓ/ም መደበኛ ፍ/ቤቱን ከፍተን ሙሌን ወንድሜን ላይመለስ ደዌ ሜዳ መቃብር ቀበርነዉ አፈር አልብሰነዉ ተመለስን። ወጣቱን ህፃኑን ሙሌን በጨካኞች፣ በሆዳሞች ተጨከነበት እኛም ጨክነን አፈር አለበስነዉ። የሙሌ ነፍስ ግን አሁን ፍትህ በማለት ትጮኻለች፣ ገድለዉት ያልረኩ፣ ሞቶም የሚፈሩት ገዳዮቹ አሁንም የፍትህን ድምፅን ለማፈን እንቅልፍ አጥተዉ እየሰሩ ነዉ። እዉነት ብትመነምንም ስለማትቆረጥ ለሙሌ ነፍስ ቀን ወጥቶ ፍትህ ሰፍኖ በስልጣኑና በገንዘቡ ያበጠዉ ከርከሮም ተገንድሶ ወድቆ እናያለን።

📌 በጣም የሚያሳዝነውና የሚያበሳጨው ግን አንድ ከፍተኛ የመንግስት ባለ ስልጣን ሙቶ ምን ላግዛችሁ አስፈላጊውን ትብብርና ድጋፍ ላድርግላችሁ ብሎ የሚጠይቀን የመንግስት አካል መጥፋቱ ነው። የደሴ ከተማ አስተዳደር የሚያሳየዉ ዳተኝነት ነገ በየቤታችሁ የሚያንኳኳ ግፍ ነዉ።

ወርቃማ ንግግሮች

26 Oct, 18:20


ልብ የሚነካ የሙሉጌታ ከበዴ የግድያ ታሪክ😳😢
_______
በሬ ካራጁ ከመዋሉ በፊት፣ የገዳዮቹን ዱለታ ያልተረዳዉ ሟች የተደገሰለትን የዕለቱን የሞት ድግስ አያዉቅም፣ መንፈስ የተረዳ ይመስል ሰሞኑን ስለመኖር ከንቱነት የዚች ዓለም ኑሮ ኮንትራትነት ከሃይማኖታዊ አስተምሮ እያጣቀሰ ጓዴኞቹን ሲያወራ ሳምንቱን አሳልፏል። ቅዳሜና ዕሁድን ለቤተሰቡ የሰጠዉ ወጣቱ ዳኛ ሙሉጌታ ከበዴ የገዳዮችን ካራ እየተሳለበት መሆኑን አልተረዳም፣ በሱ ላይ የሚያሾከሽኩ፣ ጨለማን ተገን አድርገዉ የሚመክሩ ሰዉ በላዎች በመንገዳችን ላይ ሆነብን ብለዉ የሚያስቡ ሰዉ በላዎች በየሰርጣ ሰርጡ ሙሉጌታን ስለማስወገድ የሚመክሩ የተንኮል ድምፆችን አይሰማም፣ ሙሌ ልበ ብርሃን ቀና አሳቢ ነዉ፣ በሙሉጌታ ልብ የሚታሰቡት ፍቅር ፍትሃዊነት እንጂ ሰዉ በላዎች ሊጠረጥር ይቅርና ሰዎችን መበደል ልቡን የሚያሳዝነዉ ልጅ ነዉ። እንዲህ አይነት አረመኔነትን አይጠረጥርም፣ የሰዉ ጅቦች ድምጽን መስማት የሚችል ጆሮ የለዉም።

ዕለተ ሰኞ መደበኛ ፍ/ቤት የሚከፈትበት ዕለት ነዉ፣ በማያዉቀዉ መልኩም በሱ ላይ ካራ ሲስሉ የነበሩ ሴረኞችንም ያገናኜች ዕለት ነበረች። ሙሌ ጥቅምት 04/2017 መደበኛ ስራዉን ለመከወንና የዓመቱን የፍ/ቤት መደበኛ ስራ መከፈትን በማስመልከት ደመቅ ብሎ የወጣበት ዕለት ነዉ። ከቤት ከመዉጣቱ በፊት በእንግድነት የመጡ ቤተሰቦቹንና ጓዴኞቹን ሞቅ ባለ ጨዎታ ሸኝቷል። ቢሮዉ ሲገባ ከጥበቃ ሰራተኞችና ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ሰላምታ ሳይሆን የናፍቆት ቀልድን ጭምር የሚለዋዎጠዉ ሰብሳቢ ዳኛ ሙሉጌታ የእለት ስራ ዕቅዱን በሚኒ ማስታወሻ ላይ ከመዘገባ በኋላ ቡና ለመጠጣት በሽሚዝ ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ከቢሮ አቅራቢያ በምትገኝ የጀበና ቡና እየጠጣ የዚህ ዓመት ስራ ዕቅዳቸዉን ያወራሉ፣ በፍ/ቤቱ መዘጋት ምክናየት የፍትህ ጥያቄያቸዉ የዘገየባቸዉ ዜጎችን ግልጋሎት ለመስጠት ህልማቸዉን ይገላለፃሉ። ሙሌ ጥቅም አሳጣን መሬት አገደብን፣ የፍ/ቤት ስራን ተክተዉ ለመስራት የፈለጉ አስፈፃሚ አካላት እንደፈለጋቸዉ ለመጋለብ መሰናክል ሆነብን ብለዉ ያሰቡ ሴረኛ እባቦች ከጀርባዉ የሞት ድግሳቸዉን እንደሚያጋፍሩለት ግን ልቡ አልጠረጠረም ነበር።
ሙሌ ከዕለት ስራዎች ዉስጥ የፍትህ ተግባራትን ብቻ ሳይሆን የበጎ አድራጎት ስራዎችንም ጭምር የሚሰራ ልባም ሰዉ ነበር። በቢጫ ሚኒ ማስታወሻ ላይ የዕለት ተግባሮቹን የሰደረባቸዉን ገፅ ሳብ አድርጎ ተመለከተና “let’s go to our todays mission” አለኝ ይላል አንድ አብሮት የነበረ የስራ ባልደረባዉ፦

በአንድ ስፔሻሊቲ ሆስፒታል ተደፍራ የተኛችን ህፃን መጎብኘትና ፍትህ የምታገኝበትን መንገድ ማመቻቸት ……………
ችግር ላይ ያሉ ሁለት አቅመ ዳካሞችን ወደ ቤታቸዉ ዘልቆ መጠየቅ ……………
ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ስለ ስራ መወያየት፣ የተወሰኑ ያደሩ ስራዎችን መጎብኜትና የስራ መነቃቃትን መፍጠር
የሚሉ ተግባራቶች በዕለት ማስታሻ ደብተሩ ላይ የተመዘገቡ ዝርዝር ተግባራቶች ነበሩ።

ስራዎቹ የዚህ ዓመት የፍ/ቤት ተግባራትን ለማነቃቃትና ዓመቱን ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ለመዝለቅ እንጂ በአራጅ እጅ ነፍሱ እንደምትነጠቅ የሚያዉቀዉ ነገር የለማ። ሰዉ ያስባል ጌታ ይፈፅማል እንደሚባለዉ ሙሌ ረጅም አቅዶ የሚሰራ ከጀርባዉ ደግሞ የማያያቸዉ ግን ሁሌም የሚጠረጥራቸዉ ስዉር ባለ ረጃጅም ጥርስ ቀፈተ-ሰፊ በልተዉ የማይጠረቁ ሰይጣን ገዳዮች በየርምጃዉ እየተከተሉት ነበር።

ወጣቱ ዳኛ ሙሉጌታ እስከ ሰዓት የሚከዉነዉን ከዉኖ ለምሳ በራሱ ቤት ግብዥ ስለተደረገለት ሾፌሩን ጨምሮ ከጓዴኞቹ ጋር ወደ መኖሪያ ቤቱ አምርተዉ በሚያምርና ደስታ በተሞላበት ቤተሰባዊ ግብዣ የምሳ ሰዓት ማሳለፋቸዉን ጓዴኛዉ ይገልፃል። ሙሌ ከህፃን ልጆቹ ጋር ያለዉ ቅርርብና መስተጋብር በህፃናት አይኖች ዉስጥ የአባታቸዉን ንጉስነት፣ አይቻሌነት፣ የሚያቅተዉም ሆነ የሚያጣዉ ነገር አይኖሬነትና ገዘፍ ያለ መተማመን ይታይባቸዉ ነበር። ህፃናት በአባታቸዉ ለመጫዎት ወደ ሰማይ ሲወረወሩ የሚያሳዩት ፍልቅልቅነት በአባታቸዉ ላይ የአይሳኔነት መተማመን ሲፍለቀለቁ ይታያሉ፣ በዚያ ደረጃ የሚቀራረቡ አባትና ልጆችን ተመልክተናል ይላል በዕለቱ አብሮት የነበረዉ ጓዴኛዉ፤

ከምሳ በኋላ ወላጅ አባቱን ለመጠየቅ መገናኛ ሰፈር አምርቶ የአባቱንና የቤተሰቡን የደህንነት ሁኔታ ከጠየቀ በኋላ ጊዜ ሳያባክን ወደ ቢሮ ነበር የተመለሰዉ፣ በዕለቱ ያቀዳቸዉን የቢሮ ተግባራቶች ከሸከፈ በኋላ የዕለቱ የስራ ቀን ሲጠናቀቅ መንፈሱን ወደሚድስበትና ስለስራ ወደሚወያይበት መናፈሻ አካባቢ ሂዶ በስራ፣ በቤተሰብ ጥየቃና በበጎ አድራጎት ተግባራቶች ሲዝል የዋለዉን ሰዉነቱን ሲያፍታታ አመሼ………

ይች ምሽት የማቅ ነበረች፣ ጀንበሯ ራሱ ስትገባ ሙሌን ስማዉ የገባች ይመስላል። ለሙሌ እየጠለቀች ያለችዉ ፀሃይ ተመልሳ አትመጣም (የምሯን ነዉ)፣ ሆዳምና ቀፈታም ገዳዮቹ ከጀርባዉ እያደቡ መሆኑን ታዉቃለች ግን አንደበት ስለሌላት አትናገርም። ሙሌን ሃቀኛዉን ፍትሃዊዉን ሰዉ ቻዉ ያለች ትመስል እገሯንም እጇንም ዘርግታ ነበር የጠለቀችው።

ምሽት አንድ ሰዓት ሲሆን ከሾፌሩ ጋር ወደ ቤቱ ጉዞ ሲጀምር የሞት መላዕክ የገዳዮች ሰይፍ የተጠጋዉ መሆኑን ያልተረዳዉ ሙሉጌታ ከበዴ በነፃነት ጉዞዉን ቀጥሏል፣ የተረገመች ሰኞ ምሽት ወንድሜን የበላች ጩኻ መናገር ያቃታት፣ ከኋላ የሚያደባው የሞት መላዕክ መከላከል ያቃታት ሰኞ ምሽት ይላታል ታሪክ ነጋሪያችን እንባዉን በሶፍት እየጠረገ …………… በላተኛዋ ሰኞ ምሽት ……… እያለ ከባድ ሃዘን.........
አንድ ሰዓት አካባቢ የተደወለልኝ ስልክ ሙሉጌታን እኮ መቱት የሚል ድምፅ ሰማሁ፣ ሟርተኛ ምን ታሟርታለህ አልኩት ወላሂ በቦንብ መቱት አለኝ። የምርህን ነዉ ተጎድቷል ፈነከቱት አልኩኝ ቀለል አድርጌ…….. እኔ ያለሁበት ሰፈር ሙሌ ከወደቀበት በጣም ሩቅ ነዉ።

ጨነቀኝ ለማን ልደዉል ፈራሁ ለማን ላዉራ
ሙሌ ከተመታ በሗላ ማንም የሚደርስለትም ሆነ አይዞህ ወንድሜን ብሎ ቀና የሚያደርገውና የሚፈሰውን ደሙን የሚያስቆምለት ጓደኛ፣ወንድም፣ ዘመድ አዝማድ፣ወዳጅና የቅርብ ረዳት የሚሆነው ሰው እንኳን አላገኘም ነበር። ከ40 ደቂቃ ቆይታ በኋላ ፖሊስ ሲደርስ ሙሌ ከጌታዉ ጋር ተገናኝቷል (ሁሉም ተጠናቋል)😭😭😭😭😭ኡፍ፣ ገዳይ ሰይጣን አራጆቹ በሙሌ ነፍስ ላይ ጨክነዋል፣ ሌቦች ሆዳሞች ፈጣጦች ሳያፍሩ ሙሌን ፍትሁን ገደሉት፣ ፖሊስ አስክሬኑን አፋፍሶ ሆስፒታል ወስዶታል እኔም ስደርስ ሌሎች ወንድም ወዳጆቹ ነበሩ፣ ከፍተኛ ድንጋጤ ሞቱን ያለመቀበል በመካከል ተቃቅፎ መላቀስ በቁጭት ከንፈር መብላት የተወዛገበ ስሜት እያስተናገድን ነበር።

በዚህ መካከል አደጋዉን የሰሙት ሞቱን ያረጋገጡት የደሴ ከተማ አመራሮች ከንቲባዉን ጨምሮ ማንም ዝር ያለ አካል አልነበረም፣ ሙሌን ሙቶም ይፈሩት ይሆን አንጃ እኔ …… ከጉሬያቸዉ ሁነዉ መሞቱን በፌስቡክ ያሳወጁና ያስነገሩ አካላት የሙሌ አስክሬን ሆስፒታል ተኝቶ ለማስተባበርም ሆነ ለማፅናናት በድንጋጤ የመጣ አንድም የአመራር አካል አልነበረም። አስክሬኑን ወደ ቤት ለመዉሰድ ሆስፒታሉ አንቡላንስ እንዲተባበር ጠየቅን አሁን አይወጡም ነበር ምላሻቸዉ፣ ብዙ ያገለገለዉ ፍትሃዊው ልጅ ከርከሮ ጥርስ ጅቦች ጋር የተላተመዉ ወጣቱ ዳኛ ሙሉጌታ ያገለገላት፣ ለፍትህ ጅቦችን የተጋፈጠላት ደሴ አስክሬኑን ለማድረስ የሚሆን መኪና አጣችለት፣ የግል መኪኖችም እዚሁ ደሴ እስከ 20ሺ ብር ጠየቁን፣ በመካከል ሙሉጌታ መሆኑን ያወቀ አንድ ቤተሰብ

ወርቃማ ንግግሮች

24 Oct, 17:45


በኢስራእ እና ሚዕራጅ ጊዜ ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) የወጡት ከማን ቤት ነበር?

A/ ከኡሙ ሩማን (ረ.ዐ)

B/ ከኡሙ ሃኒዒ (ረ.ዐ)

C/ ከአዒሻ (ረ.ዐ)

D/ ከኸዲጃ (ረ.ዐ)

መልስ በኮሜንት መስጫ አስቀምጡ

ወርቃማ ንግግሮች

21 Oct, 19:46


መርካቶ ሸማ ተራ በዚህ ሰዓት እየነደደ ነው።

በዱዓችሁ እያሉ ነው።

እሳቱ 3 ሰዓት በላይ ሆኖታል ሆኖም አልጠፋም ያገኘውን እየበላ እየሄደ እየተዛመተ ነው። ወንድሞቻችንን ዜሮ እያሳቀረብን ነው። በዱዓችሁ ወንድም እህቶቻችን በዱዓችሁ በዚህ ኑሮ ወላሂ እንደውም ኑሮ ከብዶቸዋል ወላሂ 😢😢😢😭

ወርቃማ ንግግሮች

21 Oct, 05:44


ማቆም የለም!

"ህልምን መከተል አዲስ ቋንቋ እንደመልመድ ነው፤ ብዙ ጊዜ እንሳሳታለን ግን እየተኮላተፍንም ቢሆን መልመዳችን አይቀርም፤ ህልምም እንደዛው ነው" ይለናል ታላቁ ደራሲ ፖውሎ ኮሊዮ።

ህልምህ ምን እንደሆነ ላላውቅ እችላለው፤ ለዛ ህልምህ መሳካት የከፈልከው መስዋዕትነትና የደረስክበትን ተስፋ መቁረጥም ላላውቅ እችላለው፤ ጥረትህን ካላቆምክ ግን እንደምታሳካው እርግጠኛ ነኝ! ወዳጄ ማቆም የሚባል ነገር የለም!

ወርቃማ ንግግሮች

18 Oct, 21:37


አስቤ አቅጄ ገደልኩት
ስሜ ሙትወኪል ይባላል። 52 ዓመቴን የያዝኩት ባለፈዉ ወር ነዉ። በትምህርት ገፍቻለሁ። በተለያዩ መስኮች 2 ማስተር ይዣለሁ። ጥሩ ስራና ገቢም አለኝ። ግን አላገባሁም። በጣም ፈሪ ሰው ነኝ። ከአባትና እናቴ ህልፈት በኋላ በሁሉም ነገር ማለት እችላለሁ ፈሪ ነኝ። ሰዉ እፈራለሁ። እንሰሳ ፡በይበልጥ አይጥንና ጨለማን በጣም ነዉ የምፈራዉ። ሴቶችን ማናገርማ የማይታሰብ ጉዳይ ነው ። በጠቅላላ የማልፈራዉና የማልሰጋዉ ነገር የለም። ነገ፡ የሚቀጥለው ቀንና ወር በጣም ነዉ የሚያሰጉኝ።
ሞትንማ አታንሱብኝ።
አባቴና እናቴ፡ አላህ የጀነት ይበላቸዉ፡ ያልወሰዱኝ ቦታና ዶክተር የለም። ያላየሁት መጽሐፍ ገላጭም የለም። ከአገር ዉጭም ለስራ ወጣ ስል የስነ ልቦና ሐኪሞች ጋር ጎራ እላለሁ። ግን ፋይዳ አላገኘሁበትም።እንዳዉም ባሰብኝ።
በዚህ ሁኔታ 52 ዓመቴን ይዣለሁ። ሰዉ ጋር በፍጹም አልሄድም።
አንድ ዶክተር የሰጠኝን ምክር ተከትዬ የዛሬ ዘጥኝ ወር ገደማ ዩኒቲ መናፈሻ ሄድኩ። ብዙ ሰዉ የለም። ከሩቅ ሁለት ሴቶች አየሁ። አንደኛዋ በዊልቸር ነዉ የምትንቀሳቀዉ። ፍጥነቴን ጨመርኩ። ቶሎ ላልፋቸዉ ሞከርኩ። የልጅቷ ሂጃብ በዊልቸሩ ጎማ ተስቦ ወደቀ።በፍጥነት አንስቼ ስሰጣት ሁለቱም በፈገግታ ብቻ አመሰገኑኝ።
እናትና ልጅ ነበሩ። ከሩቅ አያስታዉቁም። ሴትየዋ 60 ዎቹ የእድሜ ክልል ዉስጥ ይመስሉኛል።ከኔ እድሜ ብዙ አይርቁም።
እንደምንም ብዬ እያላበኝ፡ እማማ ላግዞት ስላቸዉ ፈገግ ብለው የዊልቸሩን እጅ ያለአንዳች ቃል ለቀቁልኝ።
ልጅቷን አየገፋሁ መፀዳጃ ቤት አጠገብ ስንደርስ። ይሄዉ አለቻቸው ። ፍጥነታቸዉን ጨምረው ከዓይናችን ተሰወሩ። ያኔ አሚራ መሐመድ ሰኢድ በጥያቄ ታፋጥጠኝ ጀመር። ማነህ፡ ለምን ትንተባተባለህ፡ ከማን ጋር ነዉ የመጣኸዉ። ወዘተ። አንዱንም ጥያቄ የመለስኩ አይመስለኝም። ግን መንተባተቤ ትዝ ይለኛ።
ከቦርሳዋ ወረቀትና እስክሪፕቶ አዉጥታ ፡ጫር ጫር አድርጋ ብጣቂ ወረቀት ሰጠችኝ።
ሳላየዉ እናትየዉ ብቅ አሉ።
እማዬ ስልኬን ጠይቆኝ አልሰጥም አልኩት። ከፈለክ ቤት መምጣት ትችላለህ ብዬዋለሁ ምን ይመስልሻል አለቻቸው። ደስ ይለኛል አሏት።
በፍጥነት መልካም ግዜ ብዬ መሮጥ በሚመስል አካሄድ ትቻቸዉ ሄድኩ። ሲሳሳቁ ይሰማኛል።ከመናፈሻዉ ግቢ በፍጥነት ወጣሁ።
3 ወራቶች አለፉ። አሚራ የፃፈችዉን አላነበብኩም። ሳነበዉ ሙሉ ስሟንና አድራሻዋንና ፡ እንዳትቀር የሚል መልዕክት ያዘለ ነዉ።
አልሄኩም። አራተኛዉ ወር አለፈ። በ5ተኛዉ ወር መካኒሳ አባድር መስጊድ ጀርባ መመላለስ ጀመርኩ። ሰፈራቸዉ ነዉ። ቤታቸው የትኛው ቤት እንደሆነም አወኩ። ግን ማንኳኳት አቃተኝ። አምስተኛው ወር አለፈ። በየሳምንቱ አንዴ፡ ወይንም ሁለቴ እሄዳለሁ።
አንድ ቀን ከኋላዬ፡ ሙትወኪል የሚል ድምጽ ሰማሁ እነሱ ነበሩ።
ገፍተህ ቤት አታስገባኝም አለችኝ። ገባሁ። አመሸሁ።አፌን አስከፈተችኝ። በየሳምንቱ መመላለስ ጀመርኩ። ስለፍርሃቴ ዘክዝኬ ነገርኳት። ስለማላዉቀዉ እምነቴ አስተማረችኝ። መፍራትና መስጋት ያለብን አላህን ብቻ እንደሆነ ተንትና ጋተችኝ።
የአላህ ባርያዎች ስጋት እንደማያድርባቸዉና እንደማይፈሩና ሐዘንም እነሱ ዘንድ ድርሽ እንደማይል፡ የሚናገረውን የቁርአን አንቀጽ አሳየችኝ።በሌላ አባባል የአላህ ባርያዎች ምንግዜም ደስተኞች ናቸው አለችኝ።
በሚገርም ፍጥነት ከፍርሃቴ መላቀቅና ወደ ቤቴም አምሽቼ መግባት ጀመርኩ።
የነገረችኝን ሁሉ እየጠነጠንኩ አሰብኩ። አቅጄም አስቤም ፍርሃትን ገደልኩት።ሞተ።አላንሰራራም።
ያለፈዉ ሳምንት በጥዋት ተነስቼ በራቸዉን አንኳኳህ። ዘበኛዉ ከፈተልኝ። እናትየዉ በመገረም አተኩረው አዩኝ። ምነው ልጄ ምን ነካህ ፡ በጣም ጥዋት እኮ ነው አለኝ። አልመለስኩላቸዉም። አሚራን ቀሰቀሱልኝ። ከ15 ደቂቃ በኋላ መጣች፡ አንድም ቃል ሳትተነፍስ ለትዳር እፈልግሻለሁ አልኳት።እኛ ጋር አብረህ የምትኖር ከሆነ እሺ አለች። እናቷን ትታ መሄድ አልፈለገችም። ተስማማሁ። ቤቱ በእልልታ ቀወጠ። የሚቀጥለው ሳምንት ኒካህ አስራለሁ።
ሰርግ አልፈልግም ትላለች። እኔ ግን መምህሬንና ዶክተሬን ደመቅ ባለ ሠርግ ማግባት ነው የፈለኩት። ምን ትላላቹህ።

ይላል ወንድማችን…!!!

ወርቃማ ንግግሮች

16 Oct, 05:22


   📖🌙🌙

🌹🌹🌹
         🌹🌹🌹🌹        👈አበባውን🔻
      🌹🌹🌹🌹🌹            በመንካት 🔻
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹           ጠቃሚ 🔻
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹       ነገር ያግኙ🎁
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹         🔻
      🌹🌹🌹🌹🌹             🔻
         🌿🌹🌹🌿       🔻
              🌿🌿            🔻
                 🌿                     🌿🔻
                  🌿               🌿🌿🔻
                 🌿           🌿🌿🌿🔻
                🌿      🌿🌿🌿🌿🔻
               🌿    🌿🌿🌿🌿🔻
              🌿 🌿🌿🌿🌿🔻
               🌿 🌿🌿🌿🔻
                 🌿              .🔻
                  🌿               .🔻
                   🌿                  .🔻
                    🌿                    .🔻
                    🌿
                  🌿       🌿

⚠️⚠️⚠️⚠️⚠️📡💡🌙

ወርቃማ ንግግሮች

14 Oct, 06:12


አዲስ  🔠🔠🅰️🔠🔠🔠🔠🔠🔠
ውድ የቻናላችን ቤተሰቦች ዛሬ ወደ ኸይር ስራ ላመላክታችሁ 

ከስር ያለው የኡስታዝ

muhammedsirag

📱YouTube  📱ቻናል

😚☺️🥰😚😋😋😄🥰😉
ማድረግ  ⭐️
በመቀጠልም  screenshot በኮሜንት መላክ

👇👇
https://youtube.com/@muhammedsirage
https://youtube.com/@muhammedsirage

ወርቃማ ንግግሮች

13 Oct, 21:55


~ 🍂

~ ዋጋህን ባያውቁልህ ልታዝን አይገባም ፤ ሙሉ የአንድ መንደር ህዝብ ዋጋቸውን ባለማወቁ ለሙሳና ለኸድር (ዐለይሂመሰላም) በሩን መክፈት አልፈቀደም ነበር ... አላህ ዘንድ ለሚኖርህ ዋጋ ትጋ! ሰዎችን እርሳቸው! የድብቅ ዒባዳዎችን አብዛ!
(ከዚሁ ሰፈር የዐረብኛ ፖስት የተተረጎመ)

ወርቃማ ንግግሮች

13 Oct, 21:55


👆👆👆👆

ምድር ከያዘቻቸው እንቁ የአሏህ ባሮች ውስጥ ምርጧ

የተላቀው አሏህ በዱንያም በአኺራ የላቀ ደረጃ ይስጥሽ። ላንቺም መንታ ልጆች ለመስጠት አላህ ቻይ ነውና መንታ አሳቅፎሽ ደስታሽ ሙሉ ያድርገው

ወርቃማ ንግግሮች

13 Oct, 06:59


🆘የመጀመሪያው ፕሮግራሙ
👑ርዕስ ➡️አኽላቅ


➡️በዐብዱናሲር መኑር አልጃቢሪ

🔠🔠🔠🔠

t.me/tdarna_islam?livestream
t.me/tdarna_islam?livestream

ወርቃማ ንግግሮች

10 Oct, 19:37


በኪንታሮት ህመም ለምትሰቃዩ ሁሉ
እኔ በምጥ ምክንያት ተባብሶብኝ ብዙ ተሰቃይቻለሁ መኖር እስክጠላ ድረስ በሀበሻ መድሀኒትም አስወጥቼ ነበር መልሶ ተካ ስቃዩን የምታቁ ታቁታላችሁ ድንገት ቲክቶክ ሳይ አንድ ኡስታዝ ስለኪንታሮት ያስተማረው ትኩረቴን ሳበው እድንበታለሁ ብዬ ነይቼ እሱ ባዘዘው መሰረት ሰርቼ ተጠቀምኩት ወላሂ አልሃምዱሊላህ እንደዚህ ጤንነት ተሰምቶኝ አያቅም በ5 ቀን ውስጥ ህመሙ ተወኝ አልሀምዱሊላህ እናንተም አምናችሁ ከተጠቀማችሁ ትድናላችሁ እሱም ብዙ ሰው ድኖበታል ብሏል የሚያስፈልገው 1ጥቁር አዝሙድ ዘይት(ንፁህ)እኔ ፍሬውን በደንብ ፈጭቼ ነው የተጠቀምኩት 2 ሽታ የሌለው ቫዝሊን 3 የወይራ ዘይት
መጠን ሩብ ግማሽ ሊትር ሀይላንድ የወይራ ዘይት ጥቁር አዝሙድና ቫዝሊኑን በግምት ነው ያረኩት እነዚህን አቀላቅለን 7 የቁርዓን ምዕራፎችን 7 ጊዜ መቅራት
1.ሱረቱል ፋቲሀን 7 ጊዜ ቀርተን ውህዱ ላይ 3 ጊዜ ቢስሚላህ እያልን መተንፈስ ኡፍፍ ማለት
2.አያተል ኩርሲን 7 ጊዜ ቀርተን 3 ጊዜ መተንፈስ
3. አመነ ረሱሉን 7 ጊዜ ቀርተዘን እንደዛው👆
4.ለው አንዘልና ሀዘል ቁርዓን 7 ጊዜ ቀርተን እንደዛው
5ቁልሁወላሁ አሀድ (ሱረቱል ኢኸላስ)7ጊዜ ቀርተን በተመሳሳይ
6 ቁል አኡዙ ቢረቢል ፈለቅ(ሱረቱል ፈለቅ)7 ጊዜ ቀርተን በተመሳሳይ
7 ቁል አኡዙ ቢረቢናስ(ሱረቱ ናስ )7 ጊዜ ቀርተን በተመሳሳይ ከዛ ውህዱን በደንብ ካቀላቀልነው በኋላ ማታ ማታ በቀዝቃዛ ውሃ እየታጠብን መቀባት የመጀመሪያዎቹ ቀናት ትንሽ ይለበልባል መቻል ነው ጠዋትም በውሃ ብቻ ታጥበን መቀባት ኢንሻአላህ በአጭር ቀን ትድናላችሁ በደንብ እስከሚሻላችሁ ድረስ አታቋርጡ
ማሳሰቢያ ውህዱ ቁርዓን የተቀራበት ስለሆነ ሽንት ቤት ውስጥ መቀባት አይቻልም ቁርዓኑን እራሳችሁ መቅራት ካልቻላችሁ ሌላ ሰው ይቅራላችሁ አላህ ሰበብ ያድርግላችሁ

ወርቃማ ንግግሮች

10 Oct, 06:22


ታላቅ የደዕዋ ፕሮግራም በወልቂጤ
~
የፊታችን እሁድ ጥቅምት 03/02/2017 በወልቂጤ ከተማ የደዕዋ ፕሮግራም ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።

በእለቱም :-
(1) ተውሒድ እና ሺርክ በኢብኑ ሙነወር
(2) ሱንና እና ቢድዐህ በአቡል ዐባስ
(3) አኽላቅ በዐብዱናሲር መኑር አልጃቢሪ እና
ሌሎችም እንግዶች ይሳተፋሉ፣ ኢንሻአላህ።

ለተጨማሪ መረጃ:- 0905097178 ሙራድ

በቴሌግራም ቀጥታ ስርጭት የሚተላለፍበት ቻናል
👇👇
🟢 t.me/tdarna_islam
🔴 t.me/tdarna_islam

17,139

subscribers

1,118

photos

213

videos