Tirita 97.6 FM Radio

@tiritaradio


ትርታ 97.6 ኤፍ ኤም ''ከልብዎ የቀረበ''

ትርታ ሚዲያ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ያለ የንግድ መዝናኛ፣ ዜና እና ቢዝነስ ጭብጥ ያለው ሚዲያ ነው።

Tirita 97.6 FM Radio

23 Oct, 18:47


ዛሬ ማምሻውን በአዲስ አበባ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 አዲሱ ገበያ አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ እስካሁን የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።

አደጋው በሸገር የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ መድረሱን ነው የአዲስ አበባ ፖሊስ የገለጸው። በአደጋው የተጎዱ ሰዎችን ህይወት ለመታደግ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ገልጿል።

"የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ነው" ብሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል ፥ ከሰሜን ሆቴል ወደ አዲሱ ገበያ ይሄድ የነበረ ኮድ 3 43994 ሸገር ባስ ላይ ነው አደጋው የደረሰው።

እስካሁን የ1 ሰው ህይወት አልፏል። እድሜውም ከ36 እስከ 40 የሚገመት ነው።

የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ ህክምና ተቋም ተልከዋል ብለዋል።


#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

23 Oct, 14:05


የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጨዋታ በጁባ ይካሄዳል።
***
በአፍሪካ ሀገሮች ዋንጫ (ቻን) የማጣሪያ ጨዋታ ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር የደርሶ መልስ ጨዋታዋን በደቡብ ሱዳን ጁባ እንደምታደርግ ተገለጸ፡፡

በዚሁ መሠረት የሀገራቱ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ጥቅምት 21 ቀን 2017 እና ጥቅምት 24 ቀን 2017 እንደሚከናወኑ መገለጹን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

ለጨዋታውም ዛሬ ሹመታቸው የተሰማው አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አቅርበዋል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

23 Oct, 12:18


መሳይ ተፈሪ የዋልያዎቹ አሰልጣኝ ሆነ!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ (ቻን) ማጣርያ የሚያደርጋቸው ጨዋታዎችን በአሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት እየተመራ እንዲያከናውን መወሰኑን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡

አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ላለፉት 12 ወራት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ምክትል አሰልጣኝ ሆነው ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከኤርትራ ጋር የሚያከናውናቸውን ጨዋታዎች ጨምሮ የቻን ማጣርያን በጊዜያዊ ዋና አሰልጣኝነት የሚመሩ መሆኑን ከፌዴሬሽኑ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

መሳይ ተፈሪ በክለብ ደረጃ ወላይታ ድቻን ከምስረታው ጀምሮ በፕሪምየር ሊግ ተሳታፊ እንዲሆንና በ8 ዓመት ቆይታው በ2009 የኢትዮጵያ ዋንጫን በማሳካት በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እንዲሳተፍ አስችሏል፡፡

አርባ ምንጭ ከተማን በዋና አሰልጣኝነት በመምራት በ2015 ዳግም ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ እንዲመለስም አድርጓል፡፡

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

23 Oct, 07:14


በየዓመቱ ጥቅምት 10 የሚከበረው " የዓለም የአዕምሮ ጤና ቀን " በዓለም አቀፍ ደረጃ " በሁሉም የሥራ ቦታ ቅድሚያ ለአዕምሮ ጤና ጊዜው አሁን ነው " በሚል መሪ ቃል ተከብሮ ከሳምንታት በፊት ተከብሮ መዋሉ ይታወሳል፡፡

# በዛሬው ሳምንታዊው የሰሞንኛ የሬድዮ ፕሮግራምም፤የአዕምሮ ጤና መታወክ በምን ምክንያት እና እንዴት ሊያጋጥም ይችላል?

# የአዕምሮ ጤና ህመምን እንዴት እንከላከለው?

# በዚሁ የዕምሮ ጤና ህክምና ላይ ለረጅም ዓመታት አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው አማኑኤል ሆስፒታል ያለው አቅምና የህመሙ ስፋት በምን ልክ የተጣጣመ ነው?

# በስራ ቦታዎች ላይ ቅድሚያ ለአዕምሮ ጤና ይሰጣል? ግንዛቤውስ ምን ድረስ ነው? የሚሉ እና ሌሎች ከአዕምሮ ጤና ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች በስፋት ይነሱበታል፡፡

# የዕለቱ ተጋባዥ እንግዳችን በአማኑኤል ስፔሻላይዝድ የአዕምሮ ህሙማን ሆስፒታል የስነ-ልቦና ህክምና ባለሙያ አቶ እንዳለ ማሞ ናቸው፡፡

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

21 Oct, 08:52


በአዲስ አበባ የሚካሔደውን  46ኛው የአፍሪካ እግርኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) ጠቅላላ ጉባኤ የተሳካ እንዲሆን ለማገዝ ኢትዮጵያ በሚገባ ተዘጋጅታለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ገለጹ፡፡

ጠቅላይ ሚንስትሩ ዛሬ ጠዋት የካፍ ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሞትሴፔን እና ሌሎች የስራ አስፈጻሚ ከፍተኛ አመራሮችን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸውንና እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የአደይ አበባ ስታዲየምን በጋራ መጎብኘታቸውን አስታውቀዋል፡፡

የካፍ 46ኛው ጠቅላላ ጉባኤ በነገው እለት በስካይ ላይት ሆቴል  ይካሔዳል፡፡

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

18 Oct, 15:19


ራይድ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ያላቸውን አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችል ስምምነት ተፈራረሙ፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዲጅታል ባንኪንግ ምክትል ፕሬዝዳንት  ወጋየሁ ገ/ ማርያም እንደተናገሩት ከራይድ ትራንስፖርት ጋር  የተደረገው ስምምነት በተለያዩ የዲጅታል አገልግሎቶች  የክፍያ አማራጮችን በመጠቀም ክፍያን ማሳለጥ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል ነው።

የራይድ ትራንስፖርት የሽያጭና ማርኬቲንግ  ሃላፊ  ዘላለም ጌታቸው በበኩላቸው :- ስምምነቱ ከ70 ሺህ በላይ ተሽከርካሪዎችና 5 ሚሊየን ደንበኞች ይዞ በሚሠራው ራይድ ትራንስፖርት በዲጅታል ስርአቱ  ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

18 Oct, 15:11


የታዋቂው ሩሲያዊ ደራሲ አንቷን ቼኮቭ ተውኔቶችን ስብስብ የያዘ የአማርኛ ትርጉም መፅሀፍ ለንባብ በቃ።

ጠበቃ የህግ አማካሪ እንዲሁም የቲያትር ባለሙያ በሆኑት ሳምሶን ብሬ ተተርጉሞ የቀረበው መጽሀፉ ''የወንዜ ሳቢሳና ሌሎች" በሚል ርእስ የታተመ ሲሆን:- አራት የአንቷን ቼኮቭ ዘመን ተሻጋሪ የምንግዜም ወርቃማ ስራዎች የተካተቱበት ነው።

ለቴአትርና የተውኔት ድርሰት ወዳጆች እና ለአንቷን ቼኮቭ አፍቃሪያን በስጦታነት የቀረበ እንዲሁም ለቴአትር ጥበብ ማስተማሪያነት ሊያገለግል የሚችል መፅሐፍ እንደሆነ ትናንት በምረቃ ዝግጅቱ ላይ ተነግሯል።

በእለቱም ከአንቷን ቼኮቭ ተውኔቶች ውስጥ ''የትንባሆ ጉዳት'' የተሰኘ ባለ አንድ ገቢር የአንድ ሰው አጭር ተውኔት ቀርቧል።

የመጽሀፍ ምረቃውን መቅረዝ ስነ-ኪን ከ IBEX ኢንተርቴይመንት በጋራ ያዘጋጁት ሲሆን ወጣት የኪነጥበብ ባለሞያዎችም የግጥም እና የሙዚቃ ስራዎቻቸውን አቅርበዋል።

በብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር ) አዳራሽ በተካሄደው የመጽሀፍ ምረቃ አንጋፋው ከያኒ ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) የክብር እንግዳ በመሆን ተገኝተዋል። ልዩ የምስጋና የምስክር ወረቀትም ተበርክቶላቸዋል።
 
(በንጉሱ በሪሁን)

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

18 Oct, 08:35


ሹመት ሰጥተዋል!
***
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት የሚከተሉትን ሹመቶች ሰጥተዋል።

1. ዶ/ር ጌዲዮን ጥሞቲዮስ፦ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር
2. ወ/ሮ ሰላማዊት ካሳ፦ የቱርዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር
3. ወ/ሮ ሃና አርአያስላሴ፦ የፍትህ ሚኒስቴር ሚኒስትር

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

17 Oct, 15:35


አዲስ አበባ በአፍሪካ ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት የሚያስገኘውን የቴክኖሎጂ ፈጠራ የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ውድድርን አስተናግዳ፣ ኢትዮጵያኖቹ ተወዳዳሪዎችም ሶስተኛ ደረጃን አግኝተዋል።
ውድድሩንም አብርሆት ቤተ መጽሀፍ ከ Africa 2 Silcon Valley ከተባለው ተቋም ጋር በትብብር ነው ያዘጋጀው።
"የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ለበጎ ተጽእኖ" በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው ውድድር ላይም በመጀመሪያ ከ48 የአፍሪካ ሀገሮች 4900 በላይ ተወዳዳሪዎች ተሳታፊ የሆኑበት ነበር። በየደረጃው በተካሔደው ማጣሪያም ስምንት ቡድኖች ለፍጻሜ መቅረብ ችለዋል። ተወዳዳሪዎቹ በሳይንስ ሙዚየም የፈጠራ ስራቸው አውደ ርእይ ለሶስት ቀናት የቀረበ ሲኾን፣ በትናንትናው እለት ምሽት ላይ በአድዋ ሙዚየም አሸናፊዎቹ ለሽልማት የበቁበት ስነ-ስርአት ተካሂዷል።

ሁለት አባላት ያሉት የኢትዮጵያ ቡድን በውድድሩ ሶስተኛ ደረጃን አግኝቶ የ4ሺ ዶላር ሽልማት ተበርክቶለታል።

የቡድኑ አባል እስጢፋኖስ በሀይሉ ፣ ፈጠራቸው ለተማሪዎች የጥናት ዘዴ የሚረዳ መሆኑን በተለይ ለትርታ ገልጿል። ተማሪዎች በእለታዊ የትምህርት መርሀግብር ወቅት እንዲመለስላቸው የሚፈልጉትን ጥያቄ በመተግበሪያው ምላሽ ያገኙበታል ሲል አስረድቷል።

በአፍሪካ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ውድድሩ ሁለት የቱኒዝያ ቡድኖች በፍጻሜ ውድድር አንደኛና ሁለተኛ ደረጃን አግኝተዋል።
የአብርሆት ቤተ መጽሀፍ ዳይሬክተር ኢንጂነር ውብአየሁ ማሞ አፍሪካ በቴክኖሎጂው ዘርፍ ከምእራቡ አለም ያለባትን ክፍተት ለመሙላት እንዲህ ያለው የውድድር መድረክ ለአህጉሪቱ ወጣቶች መዘጋጀታቸው አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። የአፍሪካ ችግሮችንም በራሷ ልጆች ለመፍታት እጅጉን የሚረዳ አይነተኛ መንገድ ነው" በማለት መሰል መድረኮች በቀጣይነትም ሊካሄዱ እንደሚገባ አስምረውበታል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

17 Oct, 11:55


እነ ጆን ዳንኤል ላይ የስር ፍርድ ቤት የሰጠውን የዋስትና ብይን ጠቅላይ ፍርድ ቤት አጽንቶታል።
***
"ከአውሮፕላን አንወርድም" በማለት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ተብለው የተከሰሱት ስድስት ግለሰቦች ላይ በስር ፍርድ ቤት ውድቅ የተደረገባቸውን የዋስትና ጥያቄን የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አፀና።

ከ15 ቀናት በፊት በስር ፍርድ ቤት የዋስትና ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ብይን መስጠቱ ይታወሳል።

ዮሃንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል)፣ አማኑኤል መውጫ፣ ናትናኤል ወንድወሰን፣ ኤልያስ ድሪባ፣ ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ የተባሉ ተከሳሾች ግን በጠበቆቻቸው አማካኝነት የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ መደረጉ አግባብ አለመሆኑን ጠቅሰው ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ብለው ነበር።

ይግባኝ ሰሚ ችሎቱ የይግባኝ ባዮችን አቤቱታን እና የከሳሽ ዐቃቤ ሕግ መልስ፣ የግራ ቀኝ ክርክርን መርምሮ የስር ፍርድ ቤት ዋስትና ጥያቄውን ውድቅ ማድረጉ ከህግ አንጻር ተገቢ ነው በማለት ብይኑን አጽንቷል። በመሆኑም ተከሳሾች በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን ይከታተላሉ።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

17 Oct, 10:47


በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው በ13 መዝገብ የተከሰሱ ግለሰቦች ከአንድ ዓመት እስከ 25 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ተቀጡ፡፡

በ13 የክስ መዝገብ ተከሰው የፍርድ ውሳኔ የተላለፈባቸው፡-

1ኛ. ተካ ወ/ማርያም 25 ዓመት ጽኑ እስራት እና 28 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፤ በሌላ የክስ መዝገብ ደግሞ 16 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት፣

2ኛ. ለማ ተማሮ 10 ዓመት ጽኑ እስራት፣

3ኛ. መለሰ ካህሳይ 11 ዓመት ጽኑ እስራትና 76 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

4ኛ. ደመቀች ማጉጂ 15 ዓመት እስራት እና 30 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

5ኛ. ስምኦን ተወልደ 3 ዓመት ከ7 ወር እስራት እና 4 ሺሕ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት ፣

6ኛ. ዮሃንስ ፍስሃዩ 5 ዓመት ከ7 ወር እስራትና 7 ሺሕ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት፣

7ኛ. ሀና ዲኖ 3 ዓመት ከ3 ወር እስራትና 2 ሺሕ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት፣

8ኛ. ረዳት ሳጅን መሀመድ አህመድ 6 ዓመት እና 8 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

9ኛ. ገ/ትንሳኤ ሀጎስ በ16 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት እና 80 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

10ኛ. አብዱል ሽኩር ይማም 10 ዓመት እና 11 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

11ኛ. ሙህዲን አማን መሀመድ 10 ዓመት እና 11 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

12ኛ. አብዱላዚዝ ራህመቶ ዳንቴቦ 5 ዓመት እና 6 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

13ኛ. ዘላለም ብርሃኑ 5 ዓመት እስራት እና 3 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

14ኛ. ናርዶስ ሀብቴ ደበሌ 4 ዓመት ከ5 ወር እስራት እና 3 ሺሕ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት፣

15ኛ. ፍሬሕይወት በላይ ግርማ 6 ዓመት እስራት እና 110 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት፣

16ኛ. ቅዱስ ኃ/ሚካኤል ሳምቢ 4 ዓመት ከ5 ወር እስራት እና 3 ሺሕ 500 ብር የገንዘብ ቅጣት፣

17ኛ. ሚኪያስ ተሾመ ፈጡላ 410 ሺሕ ብር የገንዘብ ቅጣት

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት በ13 የምርመራ መዝገቦች ሲታይ የቆየውን የሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር የወንጀል መዝገብ መርምሮ ጥፋተኞችን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል በሚል ከአንድ ዓመት እስከ 25 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲሁም ከ2 ሺሕ ብር እስከ 410 ሺሕ ብር የገንዘብ መቀጮ እንደወሰነባቸው የፌደራል ፖሊስ መረጃ ያሳያል።

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ

Tirita 97.6 FM Radio

17 Oct, 10:39


የአርቲስት ሰለሞን ቦጋለ "የራስ መንገድ" ፊልም በቴሌቲቪ መተግበሪያ ከዛሬ ጀምሮ ለህዝብ ለዕይታ ይቀርባል፡፡ ይህንን በማስመልከትም በዛሬው እለት በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል የፈርማ ስነ-ስርዓት ተከናውኗል።

ቴሌ ቲቪ በአጭር ጊዜ ውስጥ ለዕይታ ቀርበው የነበሩ ፊልሞችን መልሶ ለህዝብ ዕይታ እንዲበቁ በማድረግ የተሻለ አማራጭ ሆኖ እንደቀረበ የተናገሩት የኤግልላይን ቴክኖሎጂ መስራች እና ስራ አስኪያጅ በእርሱ ፍቃድ ጌታቸው ናቸው፡፡

ለአብነትም ከተመሠረተ እና ስራውን ከጀመረ ከአራት ወራት የማይበልጥ ዕደሜ ቢኖረውም ከእዚህ ቀደም በቴሌ ቲቪ ዶቃ እና ጥቁር አደይ፣ ትዝታና 6 ሰዓት ከሌሊቱ የተሰኙ ፊልሞች ለዕይታ መቅረቡን አስታውሰዋል።

መሰል ተግባራት ለሀገርና ለኪነጥበብ እድገት ያለው ሚና የላቀ ከመሆኑም በላይ የውጭ ምንዛሬን በማምጣት ሁሉም በጋራ የሚጠቀምበት መንገድ ነው ሲሉም ተናግረዋል፡፡

ይህንንም አሰራር በማሳደግ ቴሌቲቪ ላይ የሚገኙትን የተመረጡ ሀገርኛ ፊልሞችን በቅርቡ ከስልክ በተጨማሪ በቴሌቪዝን ለመመልከት የሚያስችል ስራ እያለቀ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዛሬው የፊርማ ስነ ስርዓት ላይም መሰል የኪነ ጥበብ ተባባሪ ቤተሠቦች ሊበረታቱ እንደሚገባ ደራሲና አዘጋጁ ሰለሞን ቦጋለ ተናግሯል።

በቀጣይ በቴሌ ቲቪ የውጭ ሀገር የተመረጡ ፊልሞችና ዘጋቢ ፊልሞችን በማካተት በብዙ ዘርፎች ለተመልካች እንደሚቀርብ ተገልጿል።

(አህመዲን ሸረፋ)

#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ