አደጋው በሸገር የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ መድረሱን ነው የአዲስ አበባ ፖሊስ የገለጸው። በአደጋው የተጎዱ ሰዎችን ህይወት ለመታደግ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ እንደሆነ ገልጿል።
"የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ ነው" ብሏል።
የአዲስ አበባ ከተማ ፓሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ በሰጡት ቃል ፥ ከሰሜን ሆቴል ወደ አዲሱ ገበያ ይሄድ የነበረ ኮድ 3 43994 ሸገር ባስ ላይ ነው አደጋው የደረሰው።
እስካሁን የ1 ሰው ህይወት አልፏል። እድሜውም ከ36 እስከ 40 የሚገመት ነው።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ ህክምና ተቋም ተልከዋል ብለዋል።
#ትርታ 97.6 FM #ከልብዎ_የቀረበ