አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE @betmetsahfte Channel on Telegram

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

@betmetsahfte


#የኅብርቱዋናዓላማ

፩.መንፈሳዊ መጻሕፍትን በዓላማ፤በእቅድ እንድናነባቸው፤እንድናስነብባቸው በሕይወታችን ትርጉም እንዲኖራቸው ማድረግ።

፪.ከቤተሰቦቻችን፤ዘመዶቻችን፤ወዳጆቻችን ስላነበብናቸው መጻሕፍት እነሱም ስላነበቡት መጻሕፍት ውይይት የማድረግ ልምድን ማዳበር።
፫.አንባቢ ትውልድ መፍጠር። ለአስተያየትዎ @orthokiha ይጻፉ።
https://t.me/BetMetsahfte
Cross @dawitfikr

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ (Amharic)

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ እርስዎን ፕሮሞሜቷል አንባቢ ትውልድ ለመፍጠር እና የውርደትን መረጃና መጻሕፍትን በእርስዎ ስለመረዳት፣ በአሰፋ ማንኛውንም አንድነት ወይም አለም ሰብእየን እንዴት እንደፈለገ፣ እና መለያየት ማመልከት። በዚህ እናት ቤተሰብ ስለሆነ፣ እናመዝገብና ፈጣን መረጃዎችን ተጫኖ ሲሆን። በአሰፋ ማንኛውንም እና ስራችንን መልስ ስላጠናቀቁ ነው። በዚህ ንባብ የሚሰጥ መጻሕፍት እርስዎም ጥያቄ ለመከታተል ስዩም ውይም ተከታታይ መልኩ። በተከተለው ቀጥሎ ከተገኙት ቤተሰብ እና በሚዜጋቸው እንደምታፍር ዘንድ የቅድሚያለው ተስፋ እንዳሉ ወረራችሁን ማቅረብ በሳይቶ ምርታችሁን ለማንበብ የተቃኘሉን ይሆናል።

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

18 Feb, 10:46


#ዐይነ-ልቦና የተሰኘ አዲሱ የዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው መጽሐፍ ወጥቷል።




#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

11 Feb, 11:14


#ሰው_እና_ቃል ኪዳኑ_ቅጽ_፪ የተሰኘ መጽሐፍ በመምህር ዕድሉ ወልዴ የተዘጋጀው ለሁለተኛ ግዜ ያታተመ ጥቂት ፍሬዎች አግኝተናል።

የጀርባው ዋጋው=250 ብር
አርጋኖናዊ ቅናሽ አርገን እየጠበቅን ነው ጎራ ይበሉ።

@dawitfikr ይዘዙ።


#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

10 Feb, 08:31


በዲን ዮሐንስ ጌታቸው
#ዐይነ_ልቡና_የተሰኘ_አዲስ_መጽሐፍ_በቅርብ_ይጠብቁን።

#በእግዚአብሔር_ፈቃድ_የትምህርተ_ጽድቅ_ቅጽ_ኹለት_ዐይነ_ልቡና_የተሰኘ_መጽሐፍ_በቅርቡ_በእጃችሁ_ይገባል።

በዚህ መጽሐፍ ውስጥ አራት ክፍሎች አሉት። የመጀመሪያው ክፍል ነገረ ሥጋዌን ይመለከታል። በዚህ ክፍል ውስጥ በነገረ ሥጋዌ ውስጥ የተወሰኑ የአገላለጽ ውዝግቦችን በተመለከተ እንዴት መረዳት እንዳለብን ተዳስሷል። እንደ መነሻ ይኾን ዘንድ ታስቦ ነገረ ሥጋዌን የተመለከተ መጠነኛ ገለጻ ከማድረግ ጀምሮ በነገረ ሥጋዌ ውስጥ ልንጠነቀቃቸው የሚገቡ አገላለጾችን በተመለከተ ማብራሪያ ቀርቧል። ነገረ ሥጋዌ እጅግ መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ስለ ኾነ በጥንቃቄ ሊታይ እንደሚገባ ከማሳሰብ ጋር ውዝግብ ያሥነሱ ጉዳዮችን ለማጥራትና ወጥ አረዳድ እንዲኖረን ለማገዝ ጥረት የተደረገበት ክፍል ነው። ይህን ክፍል በጥንቃቄ ያነቡት ዘንድ በትሕትና እጠይቃለሁኝ።
 
የመጽሐፉ ኹለተኛው ክፍል ምሥጢረ ጥምቀትን ይመለከታል። በዚህ ክፍል ውስጥ መናፍቃን ምሥጢረ ጥምቀትን በተመለከተ የሚያነሷቸውን ጥያቄዎች በቅደም ተከተል የተመለሰበት ክፍል ነው። ይህም ጉዳይ እጅግ በጣም መሠረታዊ ጉዳይ ነው። ምሥጢረ ጥምቀት ላይ የተዛባ አረዳድ ካለን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መግባት አንችልም። ወደ ቤተ ክርስቲያን መግቢያ በሩ ምሥጢረ ጥምቀት ነውና። ምእመናን በዚህ መሠረታዊ የክርስትና የምሥጢር ትምህርት ላይ የጠራ መረዳት እንዲኖራቸውና ከመናፍቃን ክሕደት ልቡናቸው እንዲጠበቅ ደጋግሞ መልስ መስጠቱ ተገቢ ነው። በመኾኑም በዚህ መጽሐፍ ኹለተኛ ክፍል ውስጥ "ያመነ የተጠመቀ ይድናል፣ ሐዋርያት ተጠምቀዋልን?፣ ጥምቀት በማን ስም ሊኾን ይገባዋል፣ የውኃ ጥምቀት አያስፈልግምን? ... የሕፃናት ጥምቀት አስፈላጊ ነውን?"  የሚሉ እና መሰል ጥያቄዎች ተመልሰውበታል። የዚህ ክፍል መደምደሚያ የሐሰተኛ አጥማቂዎችን መለያ በማብራራት ያበቃል።

ክፍል ሦስት ደግሞ የክህነት የመጀመሪያ ደረጃ የኾነውን ዲቍናን የሚመለከት ነው። በዚህ ዘመን ሰይጣን በክፉዎች እያደረ እንዲቃለል እያደረገ ካላቸው ዐበይት ነገሮች ውስጥ አንዱ ክህነት ነው ማለት ይቻላል። ክህነት እጅግ በጣም ሊከበር የሚገባው ታላቅ ምሥጢር ነው። በብዙዎቻችን ዘንድ በተለያዩ ምክንያቶች መነሻነት ክህነት ተገቢውን ክብር እያጣ ያለ ይመስላል። ይህ በእርግጥ በአንድ በኲል የክህነት አገልግሎትን ከሚፈጽሙ አካላት ችግር የተነሣ የመጣ ሲኾን በሌላ በኲል ደግሞ እኛ ምእመናንም ስለ ክህነት ካለን የግንዛቤ እጥረት የተነሣ ነው። ከዚህ በተጨማሪ ከውጭም ያሉ አካላት ክህነት እንዲጠላ በተለያዩ መንገዶች ብዙ ጥረቶችን አድርገዋል። ክህነትና የክህነት አገልግሎትን የሚፈጽሙ ካህናት በአግባቡ እስካልተከበሩ ድረስ ክርስቶስ አምላካችን የሠራልንን የድኅነት መንገድ በአግባቡ ማግኘት አንችልም። ክህነት ከተጠላ ምሥጢራትን በየት በኲል አግኝተን ወደ ድኅነት ልንገባ እንችላለን? ስለዚህ ከምንም በላይ ክብረ ክህነት እንዲጠበቅና ካህናትም አርአያ ክህነታቸውን ጠብቀው እንዲያገለግሉ ኹላችንም የበኩላችንን አስተዋጽኦ ልናበረክት ይገባል። በዚህ መሠረታዊ ምክንያት በዚህ መጽሐፍ በሦስተኛው ክፍል የዲቍናን ክብርና እንዴት ሊሰጥ እንደሚገባው ማብራሪያዎች ቀርበውበታል። ዲቍና ከተስተካከለ ሌሎቹ የክህነት ደረጃዎች የመስተካከል ዕድላቸው በእጅጉ ከፍ ያለ ይኾናል። ዲቍና ከተበላሸ ቅስናም ያን ተከትሎ የሚመጣ ነውና የመበላሸት ዕድሉ ሰፊ ይኾናል።

የዚህ መጽሐፍ የመጨረሻው እና አራተኛው ክፍል የተለያዩ ጉዳዮችን የያዘ ነው። በዋነኛነት በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ንጽሕና ጉዳይ የሚያትት ነው። አንዳንድ ሰዎች የእመቤታችንን ንጽሕናና ከማኅፀን ጀምሮ የመጠበቋን ጉዳይ ላለመቀበል ብዙ ምክንያቶችን ሲያነሡ ይታያል። የቅድስት ድንግል ማርያም ሰውነት ከማኅፀን ጀምሮ በመንፈስ ቅዱስ የተጠበቀ እና ለወልድ ሥጋዌ ተለይቶ የተዘጋጀ መኾኑን በተለያዩ መረጃዎች ያቀርባል። እርሷ መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ የሌለባት በረከተ ሥጋን በረከተ ነፍስን ከልጇ ዘንድ እያማለደች የምታሰጥ፣ የጎሠቆለ የአዳም ባሕርይ ያልደረሰባት፣ ንጹሕ ዘር መኾኗንና አካላዊ ቃል በሥጋዌውም ከእርሷ የነሣው ሰውነት ቅዱስና ከመርገም የተጠበቀ መኾኑን በዝርዝር ለማስረዳት የተሞከረበት ክፍል ነው። በዚህ ክፍል የመስቀልን ክብር በተመለከተ፣ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊን መጨረሻ በተመለከተ አርፏል ወይስ ተሰውሯል? የሚለውን በተመለከተና ለአብርሃም የተገለጡት ሦስቱ ሰዎች እነማን ናቸው የሚለውን በአበው አረዳድ ለማቅረብ ተሞክሯል።

#እባክዎትን_ለብዙዎች_እንዲዳረስ_በማድረግ_ሓላፊነትዎን_ይወጡ🙏🙏🙏

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

10 Feb, 08:30


በቅርብ ቀን ጠብቁን!!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

08 Feb, 06:51


የምሕረት በር በርስርጭት ላይ ነን!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

08 Feb, 06:44


#የምሕረት_በር_የመጽሐፍ_ዳሰሳ በወንድማችን Fitsum A Abraham

የመጽሐፍ ዳሰሳ/ Book review
     "የምሕረት በር- አንቀጸ ምሕረት"

በቤተ ክርስቲያን አገልግሎታቸውና በ"ፍካሬ ሞት ወሕይወት" በ "ጾምና ምጽዋት" መጽሐፋቸው በምናውቃቸው መምህር ቃኘው ወልዴ የተጻፈው   "የምሕረት በር" ወይም "አንቀጸ ምሕረት" የተሰኘው መጽሐፍ ርእሰ ጉዳዩን በትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ ላይ ያደረገ ሥራ  ነው። "የምሕረት በር" በ 533 ገጾች የተከተበ ድርሳን ሲሆን በውስጡም ስድስት ምዕራፎችን ይዟል።  በምክንያተ ጽሑፍነት የቀረበው #የዲያቆን #ብርሃኑ_አድማስ "ከገጠመን ችግር ለመውጣት በፍጥነት ልናደርገው የሚገባን ምንድን ነው?" በሚል ርእስ ከሦስት ዓመት በፊት በወርኃ መስከረም ማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ #Facebook ላይ የቀረበ ጽሑፍ ነው።

መምህር ቃኘው ወልዴ ይህ የመምህር ብርሃኑ አድማስ ጽሑፍ ከልባቸው እንደገባና በትንቢተ ዮናስ ላይ በእነ ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ፣ በቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ፣ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ በቅዱስ ሄሮኒመስን (ጄሮም)፣ በቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ እና መሰል ጸሐፊያን የተጻፉ የትርጓሜ ድርሳናትንና ጥናታዊ ሥራዎችን አሳድደው በጥልቀት እንዲያነቡ እንዳነሣሣቸው፣ በመጨረሻም በዚህ ሒደት ውስጥ "የምሕረት በር" የተሰኘው መጽሐፋቸው ተፀንሶ ለመወለድ እንደበቃ ይገልጻሉ።

እኔ ከዚህ በታች ለማስቀመጥ የምሞክረውን ዳሰሳ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ የመጽሐፉ ሽፋን ላይ በአጭሩ በዕውቀትና በጥበብ በጥቂት ቃላቶች ለደራሲው የሚገባ አጭር አስተያየት (blurb) አስቀምጠዋል። መምህር ያረጋል አበጋዝ ደግሞ ከአሥር ገፅ በላይ ወስዶ መቅድሙን ድንቅ አድርጎ ጽፎታል። "የምሕረት በር" መታሰቢያነቱን ያደረገው ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ስድስተኛና ለቅርብ ወዳጃቸው ለሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ነው።

"የምሕረት በር" የመጀመሪያው ምዕራፍ ስለ ትንቢተ ዮናስ መጽሐፍና በአሕዛብ ስላለች ቤተ ክርስቲያን፣ ስለ ነብዩ ዮናስ ማንነት፣ ስለ ነነዌ የደም ከተማነት፣ በመጽሐፉ ጸሐፊ ላይ ስለሚነሡ ውዥንብሮች፣ ስለ ትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ አጠቃላይ ይዘትና የአጻጻፍ ባሕርይ ይዳስሳል። ምዕራፍ ሁለት ትኩረቱን በነቢዩ ዮናስ ላይ አድርጎ ከእግዚአብሔር ስለተላለፈለት ትዕዛዝ፣ ወደ ተርሴስ በምታመራ መርከብ ስለመኮብለሉ፣ ስለተነሣው ታላቅ ነፋስ፣ የመርከቡ አለቃ በውስጠኛው የመርከቢቱ ክፍል ተኝቶ ወደነበረው ነቢዩ ዮናስ ቀርቦ፣ ከእርሱ ጋር  ስለ ተለዋወጣቸው ቃላት፣ ስለ ወጣበት ዕጣ፣ ወደ ባሕር ስለ መጣሉ ነገር ያለውን አንድምታ ገልጦ ያስረዳል።

ምዕራፍ ሦስት ነቢዩ ዮናስ በባሕር ውስጥ እያለ ስላቀረበው መሥዋዕት ይተርካል። እግዚአብሔር ታላቅ ዓሣ አንበሪን ስለ ማዘዙ፣ በአንበሪ ከርሥ ውስጥ ስለ ጸለየው ጸሎት ውስጠ ምሥጢር ያትታል። ምዕራፍ አራት ዓሣ አንበሪው በደረቅ የብስ ላይ ነቢዩን ከተፋው በኋላ ከእግዚአብሔር ዘንድ ዳግመኛ ወደዮናስ ስላመጣው መልእክት ያስተምራል።

ከዚያም ነቢዩ ዮናስ ወደ ኃጢአተኛዋ ከተማ ገብቶ "ነነዌ በሦስት ቀን ውስጥ ትገለበጣለች" በማለት በአደባባይ አሰምቶ ስለሰበከው  አስጨናቂና አስፈሪ ስብከት፣ ነነዌ የነቢዩን ቃል ሰምታ ከንስሓ ጋር ስላወጀችው ጾም፣ ስለንጉሡ ዐዋጅ፣ ስለለበሰችው ማቅ፣ በላይዋ ላይ ስለነሰነሰችው አመድና ትቢያ፣ ስለተቀበለችው ምሕረት፣ በወለተ ያዕቆብ ላይ ስለፈረደችው ፍርድ፣ እኛም እንደሀገር፣ እንደሕዝብ፣ እንደግለሰብ ልንሸሸው ስለሚገባ ቀቢጸ ተስፋ በስፋት ይነግረናል።

ምዕራፍ አምስት ነነዌ ባገኘችው ምሕረት ስለተከፋው ነቢዩ ዮናስ፣ ስለገጠመው ኀዘን፣ ወደ እግዚአብሔር ስላቀረበው አቤቱታ አዘል ጸሎት፣ እግዚአብሔርም ስለሰጠው ምላሽ በምልዓት ያትታል። ምዕራፍ ስድስት የነነዌን ታሪክ ይዞ ወደ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ይመጣል። የሰብአ ነነዌን ንስሐና በእነርሱ ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖችን በንጽጽር እያመለከተ ገንዘባችን ልናደርገው የሚገባንን የንስሓ ፍሬ ያመላክተናል።

በነቢዩ ዮናስ አንደበት ተገብቶም በቅድሚያ በትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ ላይ ለሚነሡ ጥያቄዎች ምላሽ በመስጠት መንገድ ይጠርጋል። ከዚያም ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አባቶች እስከ ምዕመናን በሀገረ ኢትዮጵያ ከመጣው የመከራ ዘመን እንደነነዌ ብሔራዊ ምሕረትን አግኝተን እንድን ዘንድ እያንዳንዳችን ልንፈጽመው የሚገባውን የንስሐ ተጋድሎ፣ ከመንፈሳዊ ምክረ ሀሳቦች ጋር ያስረዳናል።

በአጠቃላይ አንቀጸ ምሕረት (የምሕረት በር) ርእሰ ጉዳዩን በትንቢተ ዮናስ ላይ ያድርግ እንጂ ከነነዌ ጾም ባሻገር ለጥፋት ለተቃረበች ለየትኛዋም ሀገርና ሕዝቦች ታላቅ ትምህርትን የሚያስጨብጥ ድርሳን ነው። እንደ እኔ በኃጢአት ፍላጻ ለቆሰለች ነፍስም በመራራ ስብከቱ የሚያሽራት ፍቱን መድኃኒቷ ነው።

መጽሐፉ በቅዱሳን ሐዋርያነ አበውና በቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት የተጻፉ አያሌ መጻሕፍትን በማጣቀሻነት ተገልግሏል። ስለዚህም በትንቢተ ዮናስ መጽሐፍ ላይ ተበታትነው፣ በብዙ የንባብ ድካም የሚገኙ መጻሕፍትንና መጣጥፎች በአንድ ገበታ ላይ እንድናገኝ ዕድል የሚሰጥ ነው። ይህም የመምህር ቃኘው ወልዴን "የምሕረት በር" መጽሐፍ በትንቢተ ዮናስ ዙሪያ ከተጻፉ ውብ ድርሳናት መካከል በሀሳብ ጥልቀቱ ተጠቃሽ የትንቢተ ዮናስ አንድምታ (commentary) ሥራ እንዲሆን ያደርገዋል።

"የምሕረት በርን" ገዝተን ስናነብ ሰሜን ወሎ የሚገኘውን የዳውንት ሁለገብ ጉባዔ ቤት ግንባታን እየረዳንም ነውና፣ የምሕረት በርን ለራሳችንም ለወዳጆቻችንም በስጦታ መልክ ስንሰጥ በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እየመታን መሆኑ ልብ ይላል።

መምህር ቃኘው ይሄን የመሰለ ብዙ የደከምክበትን ልጅህን ገፀ በረከት አድርገህ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደሠጠህ በዘመንህ ሁሉ ክፉ አይንካህ። እናመሰግናለን ስለ መልካምነትህ ሁሉ። መልካም ንባብ!

#የምሕረት_በር_መጽሐፍ ዘወትር በመደብራችን በቅናሽ ዋጋ ያገኙታል።ይምጡ ይሸምቱ።

ለበለጠ @dawitfikr ይዘዙ።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

24 Jan, 10:35


#ከነዚ ውስጥ በጣም ያስፈልገኛል የሚሉት መጽሐፍ ይኖራል?

የትኛው እንያዝሎት?


@dawitfikr ይዘዙን


#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

18 Jan, 10:47


እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!

መልካም በዓል!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

17 Jan, 14:40


መልካም ዜና!

ቀሲስ ዶ/ር መብራቱ ኪሮስ በአዲስ መጽሐፍ ሊመጡልን ነው።

ቅዳሴ
ወደ ጌታ ደስታ የመግብያ ምሥጢር
!

የሚል ርዕስ ሰጠውታል። ከዚህ በፊት #አኰቴተ_ቊርባን የሚል መጽሐፍ ጽፈውልና።በብዝዎቻችሁ ተወዳጅ የሆነው ባለፈው ፮ኛ እትሙ አሳትመን ጥቂት ኮፒዎች እጃችን ይገኛሉ።ያላነበባችሁ አንብቡ።

ቅዳሴ ምንድነው? Linkን ተጭናችሁ 32 ገጽ በነፃ ታነቡ ዘንድ ጋብዘናል።ካነበባችሁ በኃላ ለሌሎች ማጋራት አትርሱ!!

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
ቅዳሴ ምንድነው?
https://acrobat.adobe.com/id/urn:aaid:sc:VA6C2:890bc83d-dd0a-4e36-98f0-afc953221abb
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 https://t.me/BetMetsahfte

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

17 Jan, 09:35


#ለጥምቀት ስጦታ ለማበርከት ይፈልጋሉ?


ከነዚኽ ውስጥ የትኛው መጽሐፍ ነው የፈለጉ?

ለወዳጅ ዘመድ ስጦታ ለማበርከት ሲፈልጉ
እኛ ጋር ብቅ ብለው መርጠው መራርጠው ይሸምቱ።


ለመምረጥ ከተቸገሩ እናማርጦታለን ይጎብኙን።

ለማዘዝ @dawitfikr ያነጋግሩን።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ኅብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

16 Jan, 15:36


#የመጽሐፍ ዜና

ከዚ በፊት ዮሐንስ መደብር የተሰኘ መጽሐፍ በመተርጎም የምናውቃቸው #መጋቤ ምሥጢር ያሬድ ዘርዐ ብሩክ የቅኔ መምህር የሆኑት አሁን ደግሞ በአዲስ መጽሐፍ ብቅ ብሏል።

መጽሐፉ ቅኔ መቀኘት ለሚፈልጉ ሰዎች በሙሉ የሚጠቅማቸው መጽሐፍ ሲሆን የመጽሐፉ ርእስ ደግሞ #መስተዋድ ወይም አገባብ በሚል ነው።

ይኽ መጽሐፍ የመምህሩ ተማሪዎች የሆኑ በጉጉት ሲጠብቁት የነበረ መጽሐፍ በመደብራችንም ይገኛል።

የጀርባው ዋጋው=800 ብር ሲሆን
አርጋኖናዊ ቅናሽ ደግሞ እንደተጠበቀ ነው።

ለማዘዝ @dawitfikr ያነጋግሩ።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ኅብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

16 Jan, 10:48


#ምዕላደ_ጥበብ ቅጽ ፪ ሁለተኛ እትሙ ለገበያ ውለዋል።
የኔታ በጽሐ ዓለሙ አዘጋጅተውታል።

A5
የገጽ ብዛት 490
በሽሮ ቀለም
የሽፋን ዋጋ 650ብር በስርጭት ላይ ነን!!

ዋና አከፋፋይ !
አርጋኖን መጻሕፍት መደብር
0954838117/0912044752

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር Areganon Book Store

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ኅብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

14 Jan, 16:02


#ከታተመ ቆየት ያለ መጽሐፍ።

የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ሕይወቱና ትምህርቱ የተሰኘ መጽሐፍ በመምህር ሰሎሞን በቀለ የተዘጋጀ ከታተመ ቆየት ያለ መጽሐፍ
በ 100 ብር ብቻ በመግዛት የግልዎ ያድርጉ።

ቀድመው ወደ 1000499547629 ትራንሰፈር በማድረግ ይውሰዱ።

ለበለጠ #Dawitfikr ይዘዙ። https://t.me/BetMetsahfte

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

09 Jan, 10:28


"አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ይላል ‹‹የቃና ወይን በኦሪት ሕግ ተመሰለች ፤ የጠጡአትን አላጸደቀቻቸውምና፡፡ ነገር ግን በመዓዛዋ ጣፋጭነት ልባቸውን ደስ አሰኘች፡፡ /አሰከረቻቸው ኦሪትም ቀድመው የተቀበሏትን አላጸደቀቻቸውም ፤ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል ናትና እርስዋን በመስማት ልባቸውን ደስ አሰኘች፡፡›› ‹‹ወይነ ቃናሰ ተመሰለት በሕገ ኦሪት እስመ ኢያጽደቀቶሙ ለእለ ሰተይዋ ወባሕቱ አስተፍስሐት በጣዕመ መዓዛሃ ፤ ወከማሁ ኦሪትኒ ኢያጽደቀቶሙ ለእለ ተወክፍዋ ቀዲሙ ፤ ባሕቱ አስተፍስሐት አልባቢሆሙ በአጽምኦታ እስመ ቃለ እግዚአብሔር ይእቲ››/ (አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ መጽሐፈ ምሥጢር ፯፥፭)

በኋላ የተሠጠችው መልካም የወይን ጠጅ አዲሲቱ ሕግ ወንጌል ናት፡ ፡ ስድስት ጋኖች በዚህ ሰርግ ቤት ውኃ ተሞልተው ወይን እንደተሞላባቸው በስድስተኛው ሺህ ‹እንደ ድንጋይ በፈዘዘው በሰው ልጅ ልብ ውስጥ የተሞላችው አዲሲቱ ወይን ጠጅ ሕገ ወንጌል ነበረች፡፡ አሳዳሪው ደግሞ በሰማያዊው ሰርግ ቤት ሁሉን በእቅፉ የሚያስተናግደው እንግዳ ተቀባዩ አብርሃም ነው፡፡ የቃናው አሳዳሪ ወይኑን ቀምሶ ደስ ሲለው «ሰው አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል ፤ ከሰከሩ በኋላ መናኛውን ፤ አንተ ግን መልካሙን የወይን ጠጅ እስካሁን አቆይተሃል!›› ብሎ ለሙሽራው ተናግሮ ነበር፡፡ አብርሃምም አዲሲቱን የክርስቶስ ወንጌል ባየ ጊዜ ተደስቶ ለሙሽራው ክርስቶስ «መልካሚቱን ሕግ እስካሁን አቆይተሃል!›› ብሎ አድንቋል፡፡ «አባታችሁ አብርሃም ቀኔን ያይ ዘንድ ሐሴትን አደረገ ፤ አየም ደስም አለው›› "
ከገጽ 166 የተወሰደ!

ቃና ዘገሊላ
የሽፋን ዋጋ 250ብር
በማከፋፈል ላይ ነን!

0954838117/0912044752/0925421700

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

06 Jan, 10:10


No one can explain the mystery of his birth, nor is it possible to explain
His corporeal birth was in time, but his divine Son ship was before time. The one was from a virgin mother, the other from God the Father.
The virgin held in her womb what the whole world could not contain. accepted being called the son of David so as to make you the Son of God! He allowed a slave to become His father, so as to make you who is a slave having the Lord as your father! He was born in the flesh so as to give you birth according to the spirit! He was born of a woman so you would no longer be a son to a woman!

Wish you happy Christmas

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

27 Dec, 13:53


#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት

"ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡"
ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ

ይህ ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ግሩም የሆነ መጽሐፍ አሁን በድጋሚ ታትሞ በ600 ብር የሽፋን ዋጋ ለገበያ ቀርቧል።
@dawitfikr ይዘዙት!!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

26 Dec, 20:08


፬.፪.፬.፩.ተከሥቶውን ለምን እንጠብቀዋለን?
፩. አምላካዊ አደራ ስለሆነ

አምላካዊ አደራ ስለሆነ ከመምህርነት ሌባ ወንበዴዎች እንጠብቀዋለን። በርቱዕ ትምህርት ወንጌል በርነት የማይገባ ማንኛቸውም #ሰዋዊ ግላዊ ሐሳብ ሌብነት ነውና። በተግሣጽ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ "ከተሰጠው በሃይማኖቱ ላይ የጨመረ ደፍሮ የቀነሰም ሌባ ይባላል" እንደ ተባለ በክርስቲያኖች ልቡና የተሣለው ሥዕል፣ የተሰመረው መሥመር፣ የተዘራው ዘር እስከ መጽአት ድረስ የምንጓዝበት ሐሳብ ጽድቅ ነውና ማንም ሊያማስነው ወይም ሊያጠፋው ሊያደብሰው ሊደመስሰው አይችልም። "ዘኢቦአ እንተ አንቀጽ ውስተ አፀደ አባግዕ ወዓርገ እንተ ካልእ ገጽ ሠራቂ ወፈያት ወጉህልያ ውእቱ - በጎች ወደአሉበት በበጎች በር የማይገባ ሌባ ወንበዴ ነው" ዮሐ.፲፥፩ ብሎ አምላካችን እንደነገረን የበጎች በር የተባለ የመጀመሪያ ትንቢተ ነብያት ነው። አምላካችን በነቢያት ትንቢት መሠረት ሰው መሆኑ ትንቢታቸውን እንዳልናቀባቸው ያሳያል።
የትንቢተ ነብያትን በር አድርጎ የማይገባ ሁሉ የትንቢት ሌባ ወንበዴ ነው። ....

እኛስ ታዲያ ምን እንላለን? የሃይማኖታችን መሠረት የሆነውን በነብያት ፣ በሐዋርያት የተነገረውን በሐዋርያት በተመሠረተችው በአንዲት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እናምናለን እንታመናለን።
ከአባቶቻችን በቅብብሎሽ የተቀበልናትን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖታችንን ዛሬም አንለቅም።
በዚህ በር ያልገባ ሁሉ መምህርም ነኝ የሚል ሌባ ወንበዴ ነው አለ ! እውነት ነው ይህቺ መጽሐፍ ግን እንዴት ያለች ናት? ...
ምዕራፍ ፬ገጽ ፻፶፯
🙏🙏

ነገ እና ቅዳሜ ለሚገዙ 900ብር ብቻ።የጀርባ ዋጋው 1250ብር ነው።
@dawitfikr ይዘዙ!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

24 Dec, 12:40


የኤፌሶን ወንዝ ፪ኛ ዙር ስርጭት ላይ ነን!

ዋና አከፋፋይ አርጋኖን መጻሕፍት መደብር !

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

20 Dec, 12:03


የየኔታ በጽሐ ዓለሙ መጻሕፍት የሆኑት #ታኦዶኮስ እና #ፍትሐ_ነገሥት_ምን_አለ? በስርጭት ላይ ነን።

የጀርባ ዋጋ 350/350ብር

ዋና አከፋፋይ #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

12 Dec, 05:59


#አሐቲ ድንግል ሦስተኛ እትም ወጥታለች።
ዘወትር በአርጋኖን መጻሕፍት መደብር በቅናሽ ያገኛሉ።

@dawitfikr ይዘዙ።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

06 Dec, 13:18


#እያከፋፈልን_ነው!
በብዙ ምዕመናን ጥያቄ በመምህር Henok Haile ፍቃድ ተወዳጅዎ #ቃና_ዘገሊላ መጽሐፍ 11ኛ ዕትም ለኅትመት በቅታለች።

በቃና ዘገሊላ መጽሐፍ ውስጥ ቅዱሳት መጻሕፍትን መሪ አድርገን በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት ውስጥ እንመላለሳለን፡፡ ከጌታችንና ከሐዋርያቱ ጋር ወደ ሰርግ ቤቱ እንገባለን፡፡ ወደ ጓዳ ዘልቀን የወይኑን ማለቅ አስበን እንጨነቃለን ፣ እመቤታችን ስታማልድ ልጇም ሲማለድ እናያለን ፣ ከአገልጋዮቹ ጋር ውኃ ልንቀዳ ወንዝ እንወርዳለን፡፡ አብረን ውኃውን እስከአፉ ሞልተን ጌታችን የሚያደርገውን እንጠብቃለን፡፡ ከታዳሚዎች ጋር ወይን የሆነውን ውኃ ቀምሰን እናደንቃለን፡፡ መልካሙ የወይን ጠጅ ምነው እስካሁን ቆየ? ብለን ከአሳዳሪው ጋር አብረን እንቆጫለን፡፡ ከዚያም ከሐዋርያቱ ጋር በስሙ አምነን ከሰርግ ቤቱ እንወጣለን፡፡ ከምድራዊው ሰርግ ቤት ወጥተንም ወደ የቤታችን ሳንገባ ወደ ሌላ ሰማያዊ ሰርግ በዚሁ መጽሐፍ ውስጥ እንታደማለን፡፡

የሽፋን ዋጋ 250ብር

ዋና አከፋፋይ
አርጋኖን መጻሕፍት መደብር Areganon Book Store
0954838117/0925421700

ለማዘዝ @dawitfikr ያነጋግሩ።

አድራሻ፡

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ።

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

03 Dec, 07:56


https://t.me/BetMetsahfte

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

02 Dec, 16:12


📍 #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

📱 https://t.me/BetMetsahfte

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

02 Dec, 08:52


#ወደ_ገላትያ_ሰዎች በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሐተታ በማከፋፈል ላይ ነን!

#በማከፋፈል ላይ ነን።

የሽፋን ዋጋ 350ብር ቅድምያ ለሚከፍሉ ታላቅ ቅናሽ አለው @dawitfikr ይዘዙት!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

28 Nov, 15:35


#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት

ዘአወፈየኒ አወፈይኩከ-፦
                የሰጠኝን ሰጠሁህ"
ውድ ኦርቶዶክሳውያን በብዙ ፈተና ውስጥ ሁኘ ባለችኝ ትንሽ ጊዜ በትንሿ መረዳቴ ይሄንንን መጽሐፍ፦" #ከመዝ_ነአምን " በሚል ርዕስ
ለማበርከት ሞክሬያለሁ።
ኦርቶዶክሳዊነትን ለማስረዳት በተቻለኝ መጠን የደከምሁበት ቢሆንም ከአጠገቤ መጻሕፍትን ባለማግኘቴ ግን እንደ ሚገባ ጽፌዋለሁ ብየ አላስብም።
ስለሆነም ርቱዓን ኦርቶዶክሳውያን የጠመመውን አቃንታችሁ፣የጎደለውን ሞልታችሁ፣የገደፍሁትን አርትታችሁ እንድታነቡት እማፀናለሁ።ግድፈተ ቃለ ካለም ግድፈቱ የእኔ ብቻ ነው እንጂ የቤተ ክርስቲያኗ አይደለም።
ከመጀመሪያው ጀምሮ አንብበን ከጨረስን በኋላ ቆም ብለን ወደ ኋላ ብናስበው ለአባቶች
ትምህርት መግቢያ የሚሆነንን የኦርቶዶክሳዊነት መነሻ ትምህርት እናገኝበታለን ብየ ተስፋ አደርጋለሁ።
የእኔ ደስታየ አንብበን ወደ ላይ ወደ አባቶቻችን ሐዋርያት በኅሊና ደርሰን ለልቡናችን
ድጋፍ የሚሆን ኦርቶዶክሳዊ መረዳትን ካገኘንበት ነው።
ስለሁሉም ነገር አሁን በመንፈሳዊ ተጋድሎ ላለው ትውልድ እና ከእኔ በኋላ ለሚነሣው
ትውልድ ኦርቶዶክሳዊ ሐሳቤን በጽሑፍ እንዳስተላልፍ የረዳኝን እግዚአብሔርን
አመሰግነዋለሁ።
“ጸልዩ ለነ ከመ ይሩጽ ቃለ እግዚአብሔር” ፪ ተሰ ፫፥፩

መምህር ገብረ መድኅን እንየው

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

በስርጭት ላይ ነን!!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

27 Nov, 09:32


#ከኖኅ_ጥፋት_ውኃ_በስተጀርባ
(ነገረ መለኮታዊ እና ሳይንሳዊ ሐተታ)

አዘጋጅ ዲያቆን ዶ/ር Abinet Tesfu
የገጽ ብዛት 480
2014በላይ ዋቢ መጻሕፍት
የጀርባ ዋጋ 650ብር

በብዙ ድካም፤ጥናት በጥሩ ዝግጅት ከኖኅ ዘመን ጥፋት አሁን ያለንበት ሁኔታ፤መርከባችን ቅድስት ቤተ ክርስትያን፤መጽሐፍ ቅዱሳዊ የእንስሳት ሥነ ምደባ፤የጥፋት ውኃው እና የሥነ ምድር ሳይንስ፤ካሁን ካለነው ዘመን መመሳሰል ምን ያመጣብን ይሆን?
እያንዳንዱ ጉዳይ በመንፈሳዊው እና በሳይንሳዊ ዐይን የምናይበት ግሩም መጽሐፍ ተዘጋጅቶልናል።

መጽሐፉ በ አርጋኖን መጻሕፍት መደብር Areganon Book Store ይከፋፈላል።

0954838117/0912044252

አንድ ኮፒ ምትፈልጉ @dawitfikr እዘዙት!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

26 Nov, 15:25


በማከፋፈል ላይ ነን!

ቃና ዘገሊላ ቀጣይ ሳምንት

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

25 Nov, 18:18


እንኳን ለመምህረ ዓለም ለአፈ በረከት አፈ መአዛ አፈ ጳዝዮን አፈ መዓር ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ፍልሰተ አጽም በሰላም አደረሰዎ ቅዱሱን ከወደዱት 5 ደቂቃ ብቻ ስጡን የፍቅርዎን መግለጫ  ሙሉ ገቢው በጦርነት ምክንያት ጣራው ሳይቀር ፈርሶ በችግር ላይ ላለው ራያ ቆቦ ወረዳ የኤፍራታ (የአረቋቱ) ደብረ መዊዕ ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አንድነት ገዳም የሆነውን ዝማሬ Etart media ላይ በመስማት ይደግፉ 👇
ይሄው ሊንክ

https://youtu.be/MBKSklYDrmk?si=EltgbSJvHVCm09cW 

ብቻዎን እንዳይሰሙ በአዛኝቷ  ከቻሉ ለሙሉ contact ካልሆነ ቢያንስ ይሄን መልእክት ለ10 ሰው ያጋሩልን 🥹


ገዳሙ ለመርዳት
CBE
1000037590766
@orthokiha

https://t.me/BetMetsahfte

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

23 Nov, 03:51


"ምስክሮችህ ድንቆች ናቸው፤ ስለዚህ ነፍሴ ፈለገቻቸው።"
መዝሙር ፻፲፰ ቊጥር ፻፳፱

ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ያሬድ ለኅዳር ሚናስ በደረሰው ዝማሬ ላይ "ንሕነሰ ብነ ሰማዕት ዘየዓውዱነ ከመ ደመና ንግድፍ እምላዕሌነ ኵሎ ክበደ ወሁከተ ኃጢአት፡፡" በማለት እንደ ተናገረው በዙሪያችን እንደ ደመና የከበቡን እጅግ በርካታ ሰማዕታት አሉን፡፡ ሕይወትን ለሰጣቸው እስከ ሞት ለወደዳቸው ለአምላካቸው ራሳቸውን መሥዋዕት አድርገው ካቀረቡ በአሚነ ክርስቶስ ታላቅ መከራ ከተቀበሉ ከቅዱሳን ሰማዕታት አንዱ ገባሬ ተአምራት ወመንክራት ማር ሚናስ ነው፡፡

ኅዳር ፲፭ ቀን የገባሬ ተአምራት የሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ በዓለ ዕረፍት ይከበራል፡፡ ቅዱስ ሚናስ በዐራተኛ መቶ ክፍለ ዘመን በሃያ ዐራት ዓመቱ ሰማዕትነትን የተቀበለ ግብፃዊ ነው፡፡ ግብፃውያን ለቅዱስ ሚናስ የተለያ ፍቅር አላቸው፡፡ ቅዱስ ሚናስን ማር ሚና(አቡ ሚና) በማለት ይጠሩታል፡፡ ማር ማለት ቅዱስ ማለት ነው፡፡ ሴትን ቅድስት ለማለት ደግሞ ማርታ ይላሉ፡፡ ቅዱስ ሚናስ አባቱ አውዶስዮስ እናቱ አውፌምያ ይባላሉ፡፡ የቅዱስ ሚናስ እናት መካን ስለነበረች በጣም ታዝን እግዚአብሔር ልጅ እንዲሰጣት ትለምን ነበር፡፡

እግዚአብሔርም የልመናዋን ቃል ሰምቶ ወንድ ልጅ ሰጣት።
ቅዱስ ሚናስ አባትና እናቱን በልጅነት ጊዜ በሞት ባጣ ጊዜ ከእነርሱ የወረሰውን ሀብት ንብረት ሸጦ ለድሆች አከፋፈለ፣ ይኽንን ዓለም ንቆ መነነ። በዘመኑ አምልኮተ ጣኦት ተስፋፍቶ ነበር፡፡ በነገሥታቱ ለጣኦት እንዲሰግድ ሲጠየቅ ለጣኦት አልሰግድም በማለቱ አንገቱን በሰይፍ ተቀልቶ የሰማዕትነት አክሊልን ተቀዳጅቷል፡፡

ምእመናን የሰማዕቱ ራስ ላይ ብዙ ሽቱ አርከፍክፈው በከበሩ ልብሶች ገንዘው በሣጥን ውስጥ አኖሩት፡፡ ቅዱስ ሚናስ አንገቱን በሰይፍ እንዲመታ ያዘዘው ንጉሥ ሥጋው በእሳት እንዲቃጠል ፈረዶበት ነበር፡፡ ነገር ግን እሳቱ በቅዱስ ሚናስ ላይ አንዳች ኃይል ስላልነበረው ከሥጋው ምንም ምን አላቃጠለም፤ በሥጋውም ላይ ምንም ምን የእሳት ቃጠሎ ምልክት አልታየበትም፤ ወዳጆቹም በዚኽ ነገር እጅግ ተደነቁ፡፡ ሰማዕቱ በሕይወተ ሥጋ ከተቀበለው መከራ ይልቅ ከዕረፍቱ በኋላ በሥጋው የደረሰበት መንገላታት ታላቅ ነው ።

የተወደደው ሰማዕት የቅዱስ ሚናስ ተጋድሎውን የፈጸመው በዘመነ ዲዮቅልጥያኖስ ኅዳር ፲፭ ቀን ፫፻፩ ዓ.ም. ነው። በዚኽን ዕለትም ታላቁ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ ምሥክር ቅዱስ ሚናስ ሦስት የድል አክሊላትን ተቀዳጀ፡፡ ዳግመኛም በዚኽን ዕለት ተወዳጁ ሰማዕት ቅዱስ ሚናስ ከድል ነሺዎች ከማኅበረ በኵር ጋር ስሙ ተጻፈ፡፡

ቅዱሳን አባቶቻችን በመጽሐፈ ሲኖዶስ ዳግመኛም በመጽሐፈ ዲድስቅልያ ታመሰተደነቁ፡፡ ደማቸውን ያፈሰሱትን፣ አንገታቸውን ለስለት፣ ዠርባቸውን ለግርፋት፣ ሰውነታቸውን ለእሳት አሳልፈው የሰጡ ቅዱሳን ሰማዕታትን መታሰቢያ እናከብር ዘንድ አዝዘውናል፡፡ በዚኽም መሠረት አንዲት፣ ቅድስት፣ ሐዋርያዊትና ኵላዊት ቤተ ክርስቲያን በሰማዕትነት ደሙ የተወደደ ልጅ የኾናትን ጣፋጭ መዓዛ ያለው ሽቱ የኾነውን ሰማዕቱን ቅዱስ ሚናስን ታከበረዋለች፤ የከበረ ስሙንም ጠርታ ታመሰግነዋለች፡፡

ከዘመነ አኲስም ዠምሮ የገባሬ ተአምር ቅዱስ ሚናስ በዓለ ዕረፍቱ ይከበራል፡፡ ማኅቶተ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ያሬድም ለኅዳር ፲፭ በደረሰው መዋሥዕት ላይ "ዘመነነ ክብረ ዘበምድር ዘበሰማያት አብደረ፤ ሚናስ ኅሩይ ሐራሁ ለክርስቶስ ሰማዕተ ኮነ በጽድቅ፡፡ (ሰማያዊውን ክብር አስበልጦ ምድራዊውን ክብር ናቀ፤ የተወደደውና የተመረጠው የክርስቶስ ወታደር ሚናስ በእውነት የክርስቶስ ምሥክር ኾነ፡፡)" በማለት እንደ ወርቅ አንከብሎ እንደ ሸማ ጠቅልሎ የሰማዕቱን ሕይወትና ተጋድሎ በአጭሩ ገልጾታል፡፡

ዳግመኛም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በዚኹ ድርሰቱ "ሚናስ ሰማዕት ኅሩይ፤ በታእካ ሰማይ ሰአል ወጸሊ በእንቲአነ፡፡ (በሰማያዊው አዳራሽ በመንግሥተ ሰማያት የተመረጥኽ ሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ስለ እኛ ለምንልን፤ ጸልይልን፡፡)" በማለት ገባሬ መንክራት ቅዱስ ሚናስ በተሰጠው ቃል ኪዳን መሠረት እንዲያማልደን፤ ጸሎቱና ረድኤቱ እንዳይለየን፣ በረከቱ እንዲያድርብንና በአማላጅነቱ እንዲጠብቀን የተማሕጸኖ ጸሎት አቅርቦለታል፡፡ እኛም ቅዱስ ያሬድን አብነት አድርገን ዘወትር ክቡር ስሙን እየጠራን "የተመረጥኽ ሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ስለ እኛ የፈጣሪህን ይቅርታና ቸርነትን ለምንልን፤ ጸጋውን እንዲያበዛልን ሥርየተ ኃጢአትን እንዲሰጠን ጸልይልን፡፡" በማለት እንማልደዋለን፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በደሙ ልጅ የኾነላትን ይኽን ታላቅ ሰማዕት ጽሌ ቀርጻ፣ ገድል ጽፋ፣ በአረፍተ መቅደስ ሥዕሉን ሥላ፣ ዕጣን በማሳረግ መሥዋዕት በመሠዋት፣ ዝክር በመዘከር ታከብረዋለች። የታላቁ ሰማዕት የቅዱስ ሚናስ በዓለ ዕረፍቱም በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት መሥዋዕት በመሠዋት፣ ዕጣን በማሳረግ፣ መብራት በማብራትና በስሙ ዝክር በመዘከር ይከበራል።

ማር ሚና በሀገራችን በጣና ቂርቆስ ከሰማዕቱ ከቅዱስ ቂርቆስና ከቅዱስ እስጢፋኖስ ጋር ቤተ መቅደስ ታንጾለት ነበር፡፡ ከባህር ዳር ከተማ በግምት ፳፫ ኪ. ሜ. ርቀት ላይ ከአቡነ ሐራ ድንግል ገዳም አካባቢ በስሙ የታነጸ ቤተ ክርስቲያን ይገኛል፡፡ በተለምዶ አካባቢውም "ሚናስ"እየተባለ ይጠራል። ገድለ አቡነ ሐራ ድንግል የቅዱስ ሚናስ ቤተ ክርስቲያን በአፄ ፋሲል ዘመነ መንግሥት መታነጹን ያስረዳል፤ በዓሉሎለ ዕረፍቱ በዚያ ይከበራል። በተጨማሪም በደብረ ዘይት (ቢሾፍቱ) ባቦጋያ መድኃኔ ዓለም፣ በለገ ጣፎ በዳሌ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ፣ በሐዋሳ በታላቅ መንፈሳዊ ሥርዐት በማኅሌት፣ በቅዳሴና በዝማሬ ይከበራል።

በግብጽ በተለያዩ ከተሞች የቅዱስ ሚናስ ቤተ ክርስቲያን ይገኛል፡፡ ብዙ ክርስቲያኖችም ልጆቻቸውን በስሙ ይጠራሉ፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ስድስተኛ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ፓትረያርክ ከመኾናቸው አስቀድሞ መጠሪያ ስማቸው አባ ሚናስ ነበር፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ ስድስተኛ ከቅዱስ ሚናስ ጋር የጠበቀ ወዳጅነት ስለ ነበራቸው በስሙ ታላቅ ገዳም አንጸው የከበረ ሥጋውን በዚያ አኑረዋል፡፡ በሰማዕቱ ማር ሚና ጸሎትና አጋዥነት ድንቅ ድንቅ ተአምራት ያደርጉ ነበር፣ ልጅ ያጡ እናቶችም በእርሱ አማላጅነት ልጆች እንዲያገኙና ስማቸውንም ሚናስ እንዲሏቸው ይነግሯቸው ነበር፡፡ ቅዱስ ሚናስ እጅግ ፈጣን ተራዳኢ ሰማዕት በመኾኑ ዛሬም ብዙዎች በጸሎቱና በአማላጅነቱ ተጠቅመናል፡፡

ቤተ ክርስቲያን ዘወትር በጸሎተ ቅዳሴ ፍጻሜ ንፍቁ ካህን "ወዕቀቦሙ ..." የሚለውን ጸሎት ሲጸልዩ በረከታቸው እንዲያድብን ከሚዘረዘሩት ሰማዕታት አንዱ ሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ነው፡፡ የሰማዕቱ ቅዱስ ሚናስ ጸሎትና በረከት ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትኹን፤ ገቢረ ተአምራቱ ፈጥኖ ይደረግልን፡፡ አሜን፡፡

የአባቶቻችን ጥርጥር የሌለባት የቀናች ሃይማኖታቸው፣ ድል የማትነሣ ተጋድሏቸው የመንግሥቱ ወራሽ እንድንኾን ያብቃን፡፡ አሜን፡፡ https://t.me/BetMetsahfte

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

23 Nov, 03:49


ቅዱስ ሚናስ ነገ ዓመታዊ ክብረ በዓሉ ነው እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ።

ዛሬ መደብራችን ለምትመጡ ገድሉ በቅናች ማግኘት ትችላላችሁ።

@dawitfikr እዘዙት!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

20 Nov, 06:53


የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ #ወደ_ገላትያ_ሰዎች ትርጓሜ መጽሐፍ ቅዳሜ ይጠብቁን!

አሳታሚ እና አከፋፋይ
አርጋኖን መጻሕፍት መደብር Areganon Book Store

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ኅብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

18 Nov, 15:34


#ገድለ-አቡነ-አላኒቆስ-ዘማይበራዝዮ-ወገድለ አቡነ-አብራንዮስ-ዘደብረ-ጥሉል-እንዳ-ኣቦና

ከዚኽ በፊት በብራና ሁኖ በግእዝ ብቻ የነበረ ገድል ወደ አማርኛ ተተርጉሞ ወጥቷል።

#ጻድቁ አባታችን አቡነ አላኒቆስ በኢትዮጵያ ሸዋ መንዝ(ተጉለት ሞላሊት) በተባለው ቦታ ከአባታቸው ከንጉሥ አጼ ይኵኖ አምላክ እና ከእናታቸው ከንግሥት ኮከብያ በ 16 መስከረም 1232 ዓ. ም ተወለዱ።
ካደጉም ወደ አቡነ ዮሐንስ ከማ ዘንድ ሄደው ማዕርገ ምንኵስና ተቀበለው በ1269 ዓ.ም
ወደ ማይ በራዝዮ ከተባለ ቅዱስ ቦታ ገቡ።
ይኽ ቅዱስ ስፍራ ከርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ወደ ሽረ 20 ኪ.ሜ ርቀት ያለው ሲሆን ከዋናው አስፓልት 3 ኪ.ሜ አለው።
ከደብረ ቦንኮል አቡነ መድሃኒነ እግዚእ ገዳም በምዕራብ በኩል ማዶ ለማዶ ይተያያሉ።
ይኽ ስፍራ በቀዳማዊ ጳጳስ አቡነ ሠላማ ከሣቴ ብርሃን እጅ ተሰይሞና ተባርኮ ታቦተ ኢየሱስ ዘማይበራዝዮ የሚል ስያሜ ተሰጥቶት በኦሪት ምኵራብነት ሲያገለግል የኖረ ሲሆን በሐዲስ ኪዳን ቤተ ክርስትያኑ ተተክሎ የነበረ ቢሆንም አቡነ አላኒቆስ ቤተ ክርስትያኑ አቅንተዉታል።

ከግዜ በኋላም የጻድቁ መታሰብያ እንዲሆን በአቡነ አላኒቆስ ስም ተሰይሞ ይገኛል።

ይኽ የጻድቁ ገድል በመደብራችን ይገኛል።


#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር
#አድራሻችን_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

18 Nov, 08:06


“ኃጢአቷን የቀበረችው ማርያም” መጽሐፍ በድጋሚ ታተመ

-በመ/ር ሥሙር አላምረው የተዘጋጀው “ኃጢአቷን የቀበረችው ማርያም” የተሰኘ መጽሐፍ ጌታን ሽቶ ስለቀቡት ማርያም ኀጥእት ብዙ ኃጢአቷን ቀብራ ብዙ ጸጋ ስላገኘችውና ማርያም እኀተ አልዓዛር ልዩነት ያስረዳል፡፡ መምህሩ “ከዚኽ በኋላ ጌታችንን ሽቱ የቀቡት ሴቶች እንዴት ሥስት ናቸው ተባለ የጋራ የቤት ሥራ ይኾነናል እንጅ አንዲት ሴት ብቻ ቀባችው ብለን የጨለማ ገልማጭ አንኾንም” ይሉናል፡፡

የመጽሐፉ አላማዎች

1) በእኅተ አልአዛር ማርያም ስም ማርያም ኃጥእት ተሠውራ እንዳትቀር ማድረግ

2)ስለ ባለሽቱ ሴቶች የግብጽ ቤ/ንና ሌሎች ተቋማት ምን አይነት ትምህርት እንዳላቸው ማሳየት

3)የተለያዩ የሊቃውንት ትርጓሜ ስለ ኃጢአተኛዋ ማርያም ምን እንደሚሉ ማስረዳት

4) የማርያም ኀጥእትን ገድል መሠረት በማድረግ የንስሐ ለቅሶዋን፣ ያጋጠማትን ፈተና እንዲሁም ገድሉ ያሉበትን የስምና የታሪክ ቅደም ተከተል ዝንፈትን መጠቆም፡፡

5)መጽሐፈ ስንክሳር የካቲት 6 የእኅተ አልዓዛር መታሰቢያ እንዳልሆነና የማርያም ዘሀገረ ናይን መታሰቢያ እንደሆነ ማስረዳት

መጽሐፉ በመጽሐፍ መደብራችንም ይገኛል።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር
አድራሻችን_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ እንገኛለን።
ለበለጠ መረጃ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

18 Nov, 07:59


አሐቲ ድንግል ጥቂት ኮፒ መጥቶልናል።

@dawitfikr እዘዙት!
ወይም 0954838117 ደውሉ!


#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

13 Nov, 14:20


#ዜና የመጽሐፍ ድጋሜ ኅትመት
#ጉባኤያት

በወንድማችን ዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ የተጻፈውና ብዙ የተደከመት ይህ መጽሐፍ፡ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከተጠራው የሐዋርያት ጉባኤ (ሲኖዶስ) ጀምሮ እስከ ገባኤ ቊስጥንጥንያ ድረስ (AD 381) የተከናወኑ ዓለም አቀፋዊ ጉባኤ ቀኖናትን አስደናቂ በሆነ መልኩ አቅርቦልናል፡፡ ዲያቆን አዶንያስ ብርሃነም ስመ ጥር የሆኑ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች (አውሳብዮስ ዘቂሳርያ፡ ሩፈኖስ፣ ሶቅርጥስ ወዘተ) የጻፏቸውን ጥንታውያን የታሪክ መዛግበት በልዩ ትጋት እያጣቀሰና ከተጨማሪ የግእዝ ምንጮች ጋር እያመሳከረ የጥንቷን ቤተ ከርስቲያን ታሪክ እንድንማር ይጋብዘናል። በየገጹ የተጠቀስት የኅዳግ ማስታወሻዎችና ዋቢ መጻሕፍት እንዲሁም ደራሲው የተከተለው ምሁራዊ የአጻጸፍ ዘዴ መጽሐፉ በሥነ መለኮት ተቋማት ውስጥ የደቀ መዛሙርት ማስተማሪያ ሆኖ እንዲመረጥ ከሚያደርጉት ተጠቃሽ መሆኑ አያዳግትም።

ይኽ መጽሐፍ በመደብራችን ማግኘት ይቻላል።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

12 Nov, 03:56


https://www.facebook.com/share/p/193vQmki14/?mibextid=oFDknk


ስለ ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገዳም (አረቋቴ ራያ ቆቦ ) 120ሺ መሰብሰቡ ሰማሁኝ ደስም አለኝ።200ሺ ብንሞላት ይሆን?የቻልነውን እናድርግ🙏

CBE

1000037590766



@orthokiha

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

10 Nov, 06:46


ባለፈው ሳምንት የኤፌሶን ወንዝ አሳትመን በስርጭት ላይ መሆናችን ይታወቃል።

የኤፌሶን ወንዝ በወንድሜ ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ተጽፎ ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ የተሰጠ ነው።

የኤፌሶን ወንዝ ስትገዙ 150ብር ለግሸን እንደሰጣችሁ ይቆጠራል።

አሁን ደግሞ ባዚልያድ የሚል መጽሐፉ ሙሉ ገቢው ለመቄዶንያ አረጋውያን እና የአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል እንዲውል ወስነዋል።መታደል ነው።

መምህር ሄኖክ ኃይሌ ዕድሜ ከጤና ይስጥልን🙏

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

08 Nov, 12:51


#በማከፋፈል ላይ ነን።

ለማዘዝ @Dawitfikr ያናግሩን።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

07 Nov, 09:04


ለእንቅልፋሞች መልካም ዜና!

በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ከኤፌሶን ወንዝ የተወሰደ!

https://www.facebook.com/share/p/18G4FyD4YA/?mibextid=oFDknk

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ! https://t.me/BetMetsahfte

አርጋኖን መጻሕፍት መደብር ARGANON BOOK STORE

07 Nov, 06:43


የ2017ዓ.ም. የመንፈሳዊ መጻሕፍት እቁባችን ዛሬ ጀምረዋል።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://t.me/+vIDCWsAOZQA1ZmI0 https://t.me/BetMetsahfte

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

05 Nov, 11:57


አሐቲ ድንግል ቀድማችሁ ለከፈላችሁ ሁሉ!

ኮሚቴዎቹ እጃችን ላይ ያለው የከፈሉ ሰዎች አሉ እያልን ማቆየታችን ትክክል እንዳልሆነ ምዕመኑ መጽሐፉ እያለ የለም ማለታችን ወንጀል እንደሆነ ነግረውን ሂደዋል።ስለዚህ የከፈላችሁ መጥታችሁ ውሰዱ።
ካልሆነ ግን ለሌሎች ምዕመናን እንዲሰጥ እናደርጋለን።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ! https://t.me/BetMetsahfte

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

04 Nov, 15:44


ስለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገዳሙ እንታደገው

https://www.facebook.com/share/p/qSc83C8wLKyN9Z6i/?mibextid=oFDknk

CBE
1000037590766

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

04 Nov, 08:06


አሐቲ ድንግል ለከፈላችሁ ብቻ ኮሚቴዎቹ ልከውልናል።ምንም ዓይነት ብር ጭማሪ ሳትከፍሉ ትወስዳላችሁ።ውሰዱ።


የከፈላችሁ ብቻ መጥታችሁ ውሰዱ።
ላልከፈሉ ከ10 ቀን በኃላ በብዛት ይወጣል ያኔ ትወስዳላችሁ ተብለናል።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

02 Nov, 06:11


#የኤፌሶን ወንዝ እያከፋፈልን ነው።


ቀድማችሁ ከፍላችሁ የነበረ መጥታችሁ ውሰዱ።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

01 Nov, 17:36


🔄 #update

📖 ለመጻሕፍት መደብሮች በሙሉ!

📱https://www.facebook.com/share/p/2M7LxGdXYDJR6Ddw/?mibextid=oFDknk


📍#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ! https://t.me/BetMetsahfte

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

01 Nov, 13:03


ለተሳተፋችሁ ሁሉም እጅግ እናመሰግናለን!!
ለጥያቄው መልስ 186 ሰዎች ተሳትፋችኃል!
በትክክል የመለሱ የመጀመርያዎቹ 10 ሰዎች ተጨማሪ 3 በራሴ ጨምራለሁ 13 ሰዎች ስም ዝርዝር!

ነገ ከአርጋኖን መጻሕፍት መደብር መጽሐፉ መውሰድ ትችላላችሁ!

1.ሠረቀ ብርሃን እስከ ለዓለም
2.ዲያቆን ጸጋ ሥላሴ
3.ባሮች እሸቱ
4.አዳነ አበበ
5.Elsa
6.Zeorthodox
7.Addis+
8.እጸ-ሕይወት እሸቱ
9.የትምጌታ ድርሻ
10.
@bababity Israel
11.ጽዮን ንጉሤ
12.ሲሎንዲስ
13.ታዴ ጎንደር MK

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

01 Nov, 12:17


ለ 10ሰዎች ሽልማት አዘጋጅተናል!!


ጥያቄ:-
የኤፍራጥስ ወንዝ የተባለው ቅዱስ ኤፍሬም ነበረ::
የግዮን ወንዝ የተባለው ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ነው::

የኤፌሶን ወንዝ ማን ነው?
@orthokiha መልስዎትን ይላኩ።

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

01 Nov, 03:58


#update
የኤፌሶን ወንዝ

ቅድምያ የከፈላችሁ ብቻ ከነገ ቅዳሜ ጀምሮ መውሰድ ትችላላችሁ።

ያልከፈላችሁ !
@Natty9119 እዘዙ!

ዋና አከፋፋይ

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

31 Oct, 16:53


#የኤፌሶን_ወንዝ! ቅዳሜ በእነዚህ መጻሕፍት መደብሮች ማግኘት ትችላላችሁ!!

#update

1ኛ.ጃፋር መጻሕፍት መደብር 1000ኮፒ
2ኛ.የኔነህ መጻሕፍት መደብር ቃሊቲ 1000ኮፒ
3ኛ.ጎንደር ማዕከል 100ኮፒ
4ኛ.አርባምንጭ 100ኮፒ
5ኛ.ሀሁ መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
6ኛ.ብራና መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
7ኛ.ሓያት ሳሪስ መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
8ኛ. ሰርዲኖን መጽሐፍ መደብር/ Sardinon Book Store 300ኮፒ
9.በላይ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
10.ጌታቸው መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
11.እንሆ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
12. ኢትዮፋጎስ መጽሐፍ ማእከል- EthioFagos Book Center 100ኮፒ
13.ተዋሕዶ መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
14.ጋሽ ይልማ ፮ኪሎ 100ኮፒ
15.ሐዋሳ ማዕከል 100ኮፒ
16.ሱመያ መርካቶ 200ኮፒ
17.ማኅደር አርጋኖን መቐለ 50ኮፒ
18.ዮሴፍ መጽ መደብር መቐለ 100ኮፒ
19.ጃፋር 4ኪሎ ቅርንጫፍ 500ኮፒ
20.ባኮስ መጽሐፍ መደብር 200ኮፒ
21.ሽታው መጽ መደብር 50ኮፒ
22.ጅማ ሰንበት ትቤት 36ኮፒ
23.አሪፍ መጻሕፍት መደብር 200ኮፒ
24.ኤዞፕ መጻሕፍት መደብር ፕያሳ 100ኮፒ
25.ተኽሌ መጻሕፍት መደብር ፕያሳ 100ኮፒ
26.ደብረ አሚን ሰ/ቤት 50ኮፒ
27.አስሜ ሲኤምሲ 100ኮፒ
38.ደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት 50ኮፒ
39.ፍሬው 6ኪሎ 150ኮፒ
40.ቀሲስ መኮንን 100ኮፒ
41.ቀሲስ አበራ 60ኮፒ
42.ነጃት 50ኮፒ
43.ማዮን 50ኮፒ
40.ልዩ 30ኮፒ
41. እግዚአብሔር ምስሌነ ሰ/ቤት 50ኮፒ
42.ገርጂ ቅድስት ማርያም ሰ/ቤት 30ኮፒ
43.ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ቤት 30ኮፒ
44.ወልድያ ሰ/ቤት 50ኮፒ
45.አዳነ ባህርዳር መጽሐፍ መደብር 200ኮፒ

0954838117 ደውለው ይዘዙ! ወይም @Natty9119 ይዘዙ!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

31 Oct, 11:11


#ይናፍቅሽ_ነበር!

የገጣሚት ትዕግሥት ጉግሣ የግጥም መድብል ለገበያ ውሏል።

በአርጋኖን መጻሕፍት መደብር እየተከፋፈለ ነው።በብዛትም በግል ማዘዝ ትችላላችሁ።

የሽፋን ዋጋ 250ብር ቅናሹ በ200ብር

@Natty9119 ይዘዙ!!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

30 Oct, 17:01


#update "አሐቲ ድንግል መጽሐፍ" ቀድማችሁ ከፍላችሁ የነበራችሁ ደንበኞቻችን ነገር ግን በተለያየ ምክንያት ያልወሰዳችሁ መጽሐፍዋ አሁንም አልቃለችና ከነገ ጥዋት ጀምራችሁ አትምጡ።

መጥቷል መጥታችሁ ውሰዱ ብለን እስክንለጥፍ ድረስ ትንሽ ቀናት ታገሱን።ከታላቅ ይቅርታ ጋር🙏


#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

30 Oct, 10:50


ከነጋዴዎች ትእዛዝ ተቀብለን ጨርሰናል።ቅዳሜ የከፈላችሁበት ደረሰኝ ይዛችሁ መጽሐፉ መውሰድ ትችላላችሁ።

ለውድ አባሎቻችን ቅድምያ ማስከፈል ጀምረናል።


#የኤፌሶን_ወንዝ
👉🏻 የገፅ ብዛት 268
👉🏻 የሽፋን ዋጋ 400ብር
👉🏻 21 ስብከቶችና ዘለግ ያሉ ጥናታዊ ጽሑፎች


ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ሕንፃ ቤተ መቅደስ እድሳት የሚውል።

ቅናሹ በ330ብር
በ CBE
1000499547629
BOA
1365
AHADU BANK
0055656110101

Snrenshot ለወንድማችን ናቲ @Natty9119 ብቻ ላኩ።ምትወስዱበት ኮድ ይሰጣችኃል።

አድራሻ
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

29 Oct, 16:31


#update

የኤፌሶን ወንዝ 6786ኮፒ ትእዛዝ ተቀብለናል።

1ኛ.ጃፋር መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
2ኛ.የኔነህ መጻሕፍት መደብር ቃሊቲ 1000ኮፒ
3ኛ.ጎንደር ማዕከል 100ኮፒ
4ኛ.አርባምንጭ 100ኮፒ
5ኛ.ሀሁ መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
6ኛ.ብራና መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
7ኛ.ሓያት ሳሪስ መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
8ኛ. ሰርዲኖን መጽሐፍ መደብር/ Sardinon Book Store  300ኮፒ
9.በላይ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
10.ጌታቸው መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
11.እንሆ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
12. ኢትዮፋጎስ መጽሐፍ ማእከል- EthioFagos Book Center 100ኮፒ
13.ተዋሕዶ መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
14.ጋሽ ይልማ ፮ኪሎ 100ኮፒ
15.ሐዋሳ ማዕከል 100ኮፒ
16.ሱመያ መርካቶ 200ኮፒ
17.ማኅደር አርጋኖን መቐለ 50ኮፒ
18.ዮሴፍ መጽ መደብር መቐለ 100ኮፒ
19.ጃፋር 4ኪሎ ቅርንጫፍ 500ኮፒ
20.ባኮስ መጽሐፍ መደብር 200ኮፒ
21.ሽታው መጽ መደብር 50ኮፒ
22.ጅማ ሰንበት ትቤት 36ኮፒ
23.አሪፍ መጻሕፍት መደብር 200ኮፒ
24.ኤዞፕ መጻሕፍት መደብር ፕያሳ 100ኮፒ
25.ተኽሌ መጻሕፍት መደብር  ፕያሳ 100ኮፒ
26.ደብረ አሚን ሰ/ቤት 50ኮፒ
27.አስሜ ሲኤምሲ 100ኮፒ
38.ደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት 50ኮፒ
39.ፍሬው 6ኪሎ 150ኮፒ
40.ቀሲስ መኮንን 100ኮፒ
41.ቀሲስ አበራ 60ኮፒ
42.ነጃት 50ኮፒ
43.ማዮን 50ኮፒ
40.ልዩ 30ኮፒ
41. እግዚአብሔር ምስሌነ ሰ/ቤት 50ኮፒ
42.ገርጂ ቅድስት ማርያም ሰ/ቤት 30ኮፒ
43.ፍሬ ሃይማኖት ሰ/ቤት 30ኮፒ
44.ወልድያ ሰ/ቤት 50ኮፒ
45.አዳነ ባህርዳር መጽሐፍ መደብር 200ኮፒ



0954838117 ደውለው ይዘዙ!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

29 Oct, 11:58


ኦርያሬስ ከገበያ ብትጠፋም ብዙ ጊዜ የለችም ብንላችሁ 10ኮፒ አግኝተናል።

ዋጋ 200ብር
@Natty9119 ይዘዙት!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

28 Oct, 17:18


📖 ለአዲሱ ሱቃችሁ መመረቅያ ይሁንልኝ!


➡️ ኅትመቱ ከገበያ የጠፋው #ሃይማኖተ_አበው የተሰኘ መጽሐፍ መጋቤ ሐዲስ ፍቅረ ማርያም ባዘዘው ለአዲሱ ሱቃችሁ መመረቅያ ይሁንልኝ ብለው 20ኮፒ ልከውልና።

🛍 መጽሐፉ የሌላችሁ @orthokiha በማዘዝ በእጃችሁ አስገቡ።

📍 #አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

28 Oct, 16:05


ከ ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ገጽ

https://www.facebook.com/share/p/2PgWJkPyYCv4vs1m/?mibextid=oFDknk https://t.me/BetMetsahfte

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

28 Oct, 12:26


የኤፌሶን ወንዝ ቅዳሜ ለሁሉም መጽሐፍ መደብሮች ትሰራጫለች። የሽፋን ዋጋ 400ብር
ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ሕንፃ ቤተ መቅደስ እድሳት የሚውል።

መጽሐፍ መደብሮች ቀድማችሁ እዘዙ!
እስካሁን ያዘዙን!
1ኛ.ጃፋር መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
2ኛ.የኔነህ መጻሕፍት መደብር ቃሊቲ 1000ኮፒ
3ኛ.ጎንደር ማዕከል 100ኮፒ
4ኛ.አርባምንጭ 100ኮፒ
5ኛ.ሀሁ መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
6ኛ.ብራና መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
7ኛ.ሓያት ሳሪስ መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
8ኛ. ሰርዲኖን መጽሐፍ መደብር/ Sardinon Book Store 100ኮፒ
9.በላይ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
10.ጌታቸው መጻሕፍት መደብር 100ኮፒ
11.እንሆ መጻሕፍት መደብር 50ኮፒ
12. ኢትዮፋጎስ መጽሐፍ ማእከል- EthioFagos Book Center 100ኮፒ
13.ተዋሕዶ መጻሕፍት መደብር 500ኮፒ
14.ጋሽ ይልማ ፮ኪሎ 100ኮፒ
15.ሀዋሳ ማዕከል 100ኮፒ
16.ሱመያ መርካቶ 200ኮፒ
17.ማኅደር አርጋኖን መቐለ 50ኮፒ
18.ዮሴፍ መጽ መደብር መቐለ 100ኮፒ
19.ጃፋር 4ኪሎ ቅርንጫፍ 500ኮፒ
20.ባኮስ መጽሐፍ መደብር 200ኮፒ
21.ሽታው መጽ መደብር 50ኮፒ
22.ጅማ ሰንበት ትቤት 36ኮፒ
23.አሪፍ መጻሕፍት መደብር 200ኮፒ
24.ኤዞፕ መጻሕፍት መደብር ፕያሳ 100ኮፒ
25.ተኽሌ መጻሕፍት መደብር ፕያሳ 100ኮፒ
26.ደብረ አሚን ሰ/ቤት 50ኮፒ
27.አስሜ ሲኤምሲ 100ኮፒ
38.ደብረ ታቦር ጉባኤ ቤት 50ኮፒ
39.ፍሬው 6ኪሎ 150ኮፒ
40.ቀሲስ መኮንን 100ኮፒ
41.ቀሲስ አበራ 60ኮፒ
42.ነጃት 50ኮፒ
43.ማዮን 50ኮፒ
40.ልዩ 30ኮፒ



#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

28 Oct, 08:49


#update

አሐቲ ድንግል ቀድማችሁ የከፈላችሁ ከዛሬ ጀምሮ መጥታችሁ መውሰድ ትችላላችሁ።
ያልከፈላችሁ ዛሬ አትምጡ።ተጨማሪ ኮፒ ሲሰጠን እናሳውቃለን🙏

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

26 Oct, 17:04


መልዕክት ለመጽሐፍ መደብሮች እና ሰንበት ት/ቤቶች ብቻ!!

#የኤፌሶን_ወንዝ በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

ቀጣይ ሳምንት ቅዳሜ ይወጣል።

ስለዚህ ምትፈልጉት ቁጥር ቀድማችሁ አስይዙ።

@orthokiha ወይም 0912044752 ማዘዝ ትችላላችሁ🙏

ዋና አከፋፋይ አርጋኖን መጻሕፍት መደብር

ሙሉ ገቢው ለግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስትያን ሕንጻ ቤተ መቅደስ እድሳት የሚውል!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

26 Oct, 11:24


#uppate

አሐቲ ድንግል 50 ኮፒ መጥቶልናል።

ዛሬ ምትወስዱት ከኮድ 1-50 ብቻ ናችሁ።

ሰኞ ከኮድ 51-260 ያላችሁ ትወስዳላችሁ።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

26 Oct, 07:04


ትምህርት በእንተ ምክንያተ ሐውልታት

4ኛ እትም ዛሬ ወጥተዋል።

የጀርባ ዋጋ 700ብር

ቅናሹ 500ብር
CBE
1000499547629

Screenshot
@dawitfikr ይላኩ!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

25 Oct, 15:08


እግዚአብሔር ይመስገን 300 ሰዎች የመጽሐፍ እቁብ እንገባለን ብለዋል።ከታች ባለው Link ተወዳጁን!!

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇

https://t.me/+vIDCWsAOZQA1ZmI0


🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

25 Oct, 06:20


#ከገበያ ጠፍቶ የነበረ ኅብረ ሥርዓት ዘቤተ ክርስትያን ኦርቶዶክሳዊት የተሰኘ መጽሐፍ ድጋሜ ታትመዋል።

የገጹ ብዛት=554
የጀርባው ዋጋ =650

አርጋኖናዊ ቅናሽ እንደተጠበቀ ነው።

ለበለጠ @dawitfikr ይዘዙ።




#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

24 Oct, 04:49


የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ pinned «#update አሐቲ ድንግል ቅዳሜ ትወጣለች ተብለናል(ተብለናል ነው።) ለእኛ የሚሰጠን 200ኮፒ ስለሆነ እናንተ ደግሞ ይያዝልን ያላችሁን 327 ሰዎች ናችሁ ስለዚህ ቀድመው ለሚከፍሉ ብቻ እንዲወስዱት ወስነናል። መጽሐፉ ሲመጣ እንደባለፈው እንዳናስከፋችሁ ለምትከፍሉ ብቻ እንዲሆን መወሰናችን እናሳውቃለን። CBE 1000499547629 BOA 111175756 Ahadu bank 0055656110101…»

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

22 Oct, 17:25


የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ pinned «#update አሐቲ ድንግል ቅዳሜ ትወጣለች ተብለናል(ተብለናል ነው።) ለእኛ የሚሰጠን 200ኮፒ ስለሆነ እናንተ ደግሞ ይያዝልን ያላችሁን 327 ሰዎች ናችሁ ስለዚህ ቀድመው ለሚከፍሉ ብቻ እንዲወስዱት ወስነናል። መጽሐፉ ሲመጣ እንደባለፈው እንዳናስከፋችሁ ለምትከፍሉ ብቻ እንዲሆን መወሰናችን እናሳውቃለን። CBE 1000499547629 BOA 111175756 Ahadu bank 0055656110101…»

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

22 Oct, 17:24


#update

አሐቲ ድንግል ቅዳሜ ትወጣለች ተብለናል(ተብለናል ነው።)

ለእኛ የሚሰጠን 200ኮፒ ስለሆነ እናንተ ደግሞ ይያዝልን ያላችሁን 327 ሰዎች ናችሁ ስለዚህ ቀድመው ለሚከፍሉ ብቻ እንዲወስዱት ወስነናል።

መጽሐፉ ሲመጣ እንደባለፈው እንዳናስከፋችሁ ለምትከፍሉ ብቻ እንዲሆን መወሰናችን እናሳውቃለን።

CBE

1000499547629

BOA
111175756


Ahadu bank

0055656110101

የሽፋን ዋጋ 1100ብር ምታስገቡት
#900ብርብቻ

Screshoot ለዲ/ን ዳዊት ብቻ ላኩ።
@dawitfikr


N.B 200ሰዎች ሲሞላ እናሳውቃለን።ከ፪ ኮፒ በላይ አይቻልም።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0912044752_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

19 Oct, 14:55


#ከገበያ ጠፍተው የነበሩ መጻሕፍት ታትመዋል።

@dawitfikr ይዘዙ



#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0925421700_ይደውሉ

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

19 Oct, 13:42


የሚሰጡ ብፁአን ናቸው። ጥዋት በ Fb ገጼ ባደረኩት Challenge 100ሺ ተሰብስበዋል።

ሰበታ ጌቴሴማኒ ቤተ ደናግል የሁላችን ቤት ነውና

የሰጣችሁ እግዚአብሔር ያክብርልን ይስጥልን።ያልሰማችሁ ከበረከቱ ተሳተፉ!

CBE

1000003777689

AHADU BANK

00466376620303

@orthokiha

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

19 Oct, 07:44


ፋንሲ ዲኮር
ለሰርግ፣ለልደት፣ለምርቃት፣ለማንኛውም ዝግጁቶች ፋንሲ ዲኮር።
ለዲኮር ስራ፣ዲኮር እቃ ኪራይ፣ዲኮር እቃ ሽያጭ ሲፈልጉ በ +251 913543520 ወይም +251 993320132 ይደውሉልን።

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

18 Oct, 16:13


#ነገ_ቅዳሜ_ነው!

አዲሱ መደብራችን መጥታችሁ ምትጎበኙበት ቀን!

በታላቅ ቅናሽ እንጠብቃችኃለን!!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0925421700_ይደውሉ!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

18 Oct, 09:30


1.9M follower ያለው የኔታ ትዩፕ

አድራሻችን በነፃ ስላስተዋወቁልን እጅግ እናመሰግናለን።

እግዚአብሔር ያክብርልን🙏

ሌሎችም በ Tiktok ,Fb, Telegram አስተዋውቁልን!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

18 Oct, 07:45


መጽሐፍ መደብራችን ከፈረሰ በኃላ ብዙዎች ምን እናግዛችሁ? ምን እንርዳችሁ? አይዟችሁ ካላችሁን ሰዎች አንዷ መስኪ ናት።

ጋዜጠኛ መስከረም ጌቻቸው ለ
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር በነፃ ማስታወቅያ ሰርታለች።

ስለዚህ ተወዳጁ የነገረ ክርስቶስ መጽሐፍ
#ማስያስ ታላቅ ቅናሽ አድርገናል።

የሽፋን ዋጋ 480 ብር ቅናሹ
#280ብርብቻ

CBE
1000499547629
BOA
1365
AHADU BANK
0055656110101

Screenshot
@dawitfikr ይላኩ!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0925421700_ይደውሉ!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

18 Oct, 06:20


#የዕለቱ_ቅናሽ! #ጽዋዔ በመምህር Tadesse Worku
የሽፋን ዋጋ 650ብር ዛሬ መደብራችን ለሚመጡ ወይም በ Online ለሚከፍሉ
#400ብር ብቻ!

#ጽዋዔ ገጽ 256
ምዕራፍ ስምንት
#ድምፀ_ግፉዓን

"..የአንጾኪያ ዜጎች (የኢትዮጵያ ዜጎች) በሚሰሙትና በሚያዩት ብርክ ይዟቸዋል።ነጋ ጠባ የእስርና የሞት ዜና መስማት ስጋት ላይ ጥሏቸዋል።በአደጉበትና በተኳሉበት መንደራቸው የተወለወሉ ሰይፎችን የታጠቁና የተመረዙ ቀስቶችን የወደሩ ወታደሮችን ዘወትር ማየት በፍርሃት አቆራምዷቸዋል።የውዶቻቸው ከተማዋን ለቅቀው መሰደዳቸው አስጨንቋቸዋል።የራሳቸውና የልጆቻቸው ሕይወት ለከፋ አደጋ መጋለጡ አሳስቧቸዋል።
ከዚሁ ጋራ ደግሞ " ወላጆቻችን የት ናቸው? የሚሉ ልጆች ፤ልጆቻችን የትናቸው? የሚሉ ወላጆች፤ሀብት ንብረታቸው የወደመባቸው ዜጎች፤ወዳጅ ዘመድ የሞተባቸው ወገኖች፤ነገ ደግሞ ምን ይመጣ ይሆን? የሚሉ ስጉአት ሰዎችም በከተማዋ በርክተዋል።

#የእያንዳንዳችን_ቁስል_ሕመም_ከመድኃኒቱ_የተጻፈበት_ጽዋዔ(ጥሪ) አንብቡ አስነብቡ።

CBE
1000499547629
BOA
1365
Screenshot
@dawitfikr ላይ ይላኩ!
#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0925421700_ይደውሉ!
https://t.me/BetMetsahfte

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

17 Oct, 06:44


ለማስታወቅያ ተብሎ ቅናሽ የተደረገ።

#ድርሳነ_ቴዎፍሎስ ስለ እመቤታችን ድንግል ማርያም የስደቷ ነገር የሚያወሳ መጽሐፍ!

ዋጋ 195ብር ለ200ሰዎች በነጋዴዎች ሒሳብ
#በ130ብር እንዲወስዱ ፈቅደናል።
CBE
1000499547629
Screenshot
@dawitfikr ይላኩ!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ሕብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0925421700_ይደውሉ!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

16 Oct, 15:41


አሐቲ ድንግል መጽሐፍ ጨርሰናል ወደ አካውንታችን አታስገቡ።

ስለ መጣችሁ እና ስለጎበኛችሁን እጅግ እናመሰግናለን🙏


#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_የቀድሞ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ከኦሮሚያ_ህብረት_ሥራ_ባንክ_አጠገብ_0954838117_0925421700_ይደውሉ!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

16 Oct, 09:15


የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ pinned Deleted message

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

16 Oct, 07:45


የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ pinned «የርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ #አሐቲ_ድንግል በሽፋን ዋጋው 1100ብር ይምጣልን ምትሉ አሳውቁን።

ከ10ቀን በኃላ ሁለተኛ እትሙ ላይ ቅናሽ አድርገን እንሸጣለን።አሁን ያለው ለኮሚቴዎቹ በቀጥታ ገቢ የሚደረግ በከቨር ዋጋ 1100ብር ነው።
»

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

16 Oct, 06:15


የኔታ ገብረ መድኅን እንየው #ከመዝ_ነአምን ሙሉ ገቢው ለጉባኤ ቤቱ ይሁንልኝ ብለዋል።

ሁለተኛ እትሙ በሽሮ ቀለም፤በጥሩ ከቨር አሳትመን የጀርባው 1250ብር አድርገን ውል ይህ የሆነው ባለፈው የጀርባ ዋጋ ስላልጻፍን ከሱቃችን ውጪ በ1200-1500ብር ሲሸጥ ስለነበር እሱን ለመቀነስ ዋጋ ጽፈንበታል።

ትናንት
#አዲሱ_ሱቃችን ለማየት የመጣችሁ እጅግ እያመሰገን።ሱቃችን በደንብ ለማስተዋወቅ ታላቅ ቅናሽ አድርገን እንጠብቃችኃለን።

ለዛሬ ታላቅ ቅናሽ ያደረግነው
#ከመዝ_ነአምን ነው።
ዋጋ 1250ብር
ቅናሹ 900ብር ለአንድ መቶ ሰዎች ብቻ!
CBE
1000499547629
Scoreshoot
@dawitfikr ይላኩ።

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_80ሜትር_ወረድብሎ_ሪፍትቫሊ_ዪኒቨርስቲ_ሕንፃ_ላይ_0954838117_0925421700_ይደውሉ!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

14 Oct, 13:34


#ድርሳነ_ቴዎፍሎስ

በስርጭት ላይ ነን!!
የሽፋን ዋጋ 195ብር
@dawitfikr ይዘዙ!

#አርጋኖን_መጻሕፍት_መደብር_4ኪሎ_ቱሪስትሆቴል_አምባሳደር_ትክሲ_መያዣውጋር_ሄሜን_ሆስፒታል_አጠገብ_0954838117_ይደውሉ!!

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

14 Oct, 07:05


#ለውድ_ደንበኞቻችን

የክቡር ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ አዲሱ መጽሐፍ
#አሐቲ_ድንግል የመጀመሪያው ኅትመት 5ሺ ኮፒው በምርቃቱ ዕለት ስላለቀ፥ ሁለተኛውን ኅትመት በቀጣይ ሳምንት እንድትጠብቁን ከታላቅ ይቅርታ ጋር እንጠይቃለን።

በሽፋን ዋጋው መግዛት የምትፈልጉ ደግሞ ጥቂት ቅጂዎች በመጽሐፉ አስመራቂ ኮሚቴው እጅ ስለሚገኙ በ 0906654465 / 0931675567 በመደወል ማግኘት ትችላላችሁ።

የመንፈሳዊ መጻሕፍት ንባብ ቤተሰብ

14 Oct, 06:07


#የማቴዎስ ወንጌል ትርጓሜ ክፍል ፪ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በገበያ ላይ ውሏል።
የጀርባው ዋጋው =700 ብር
የገጹ ብዛት=528

አርጋኖናዊ ቅናሽ እንደተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ @dawitfikr ይዘዙ።


ወይም በ 0954838117 ይደውሉ።

17,960

subscribers

2,035

photos

66

videos