አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ @ameha_tewahdo_zcristos Channel on Telegram

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

@ameha_tewahdo_zcristos


🔔🔔🔔 አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ🔔🔔🔔
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሥርዓትን የጠበቁ ትምህርቶች ፣ወቅታዊ መረጃ፣ሥርዓተ ማኅሌት ፣ዝማሬ፣የቅዱሳንን ታሪክ የምታገኙበት ቻናል ነው።

ለማንኛውም አስተያየት @SDS12317212729

@Dn_amu_ki_17

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ (Amharic)

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሥርዓት ላይ ያለው ቻናል በትምህርት እና አዝናኝ መረጃ ለተዘጋጀው ሰዓት የሆነ ነው። በዚህ ቻናሉ የቅዱሳንን ታሪክ በማየት መጣሣሪያዊ መረጃዎችን ይከናወን። ከዚህ ቻናል የተመረጡ መረጃዎችና ከተናገሩ መረጃዎች በነጻ ማፌዢያ አድርጉ። ይህ ቤት በ@SDS12317212729 እና @Dn_amu_ki_17 አስተዳዳሪ መረጃዎችን ይመልከቱ።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

19 Feb, 07:11


#የከበረ_ሚካኤልም_ተገለጠለትና_ኃይልን_መላው

የካቲት ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው።

በዚች ዕለት ቅዱስ ሚካኤልን እግዚአብሔር ወደ ሶምሶን ላከው የፍልስጥዔም ሰዎች ሊገድሉት በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ ድል እስከ አደረጋቸውና እስከ ገደላቸው ድረስ ቅዱስ ሚካኤል ረዳው ኃይልንም ሰጥቶ በአህያ መንጋጋ አንድ ሺህ ሰዎችን ገደለ።

ተጠምቶም ለሞት በተቃረበ ጊዜም የመላእክት አለቃ ሚካኤል ተገለጠለትና አጸናው እግዚአብሔር ከአህያ መንጋጋ አጥንትም ውኃን አፈለቀለትና ጠጥቶ ዳነ።

ዳግመኛም ከሚስቱ ጋር ተስማምተው ዐይኖቹን አሳወሩ የራሱንም ጠጉር ላጩ አሠሩትም ከዚህም በኋላ ለጣዖቶቻቸው በዓልን በአዘጋጁ ጊዜ ሶምሶንን ወደ ጣዖቶቻቸው ቤት ወሰዱት በዚያም ሦስት ሺህ ያህል ሰዎች ተሰብስበው ነበር።

የከበረ ሚካኤልም ተገለጠለትና ኃይልን መላው የዚያንም ቤት ምሰሶዎች ነቀላቸው ቤቱም በላያቸው ወድቆ ከእርሱ ጋር ሁሉንም ገደላቸው ጅ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በከበረ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይማረን ለዘለዓለሙ!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

18 Feb, 15:34


አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ pinned «#ሰ_ሙ_ነ_ቅ_በ_ላ ሰሙነ ቅበላ ስንል ጾሙን ለመቀበል ሰውነትን ማዘጋጃ ሳምንት ማለት ነው ጾም ከመግባቱ በፊት ጾምን ለመቀበል ሲሰናዱ የሚቆዩበት ሰሞን ማለት ነው ቅበላ ሙሽራው ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት አስቀድሞ እንደሚገባ ኾኖ ለመቀበል የመዘጋጃ ሰሞን ማለት ነው። የምንቀበለው ሙሽራው #ዐቢይ_ጾም ነው ክርስቶስ ከእኛ ጋር እኛም ከክርስቶስ ጋር የምንዋሐድበት ፤ ክርስቶስ ከእኛ ጋር የሚያድርበት በልዩ…»

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

18 Feb, 15:33


#ሰ_ሙ_ነ_ቅ_በ_ላ

ሰሙነ ቅበላ ስንል ጾሙን ለመቀበል ሰውነትን ማዘጋጃ ሳምንት ማለት ነው ጾም ከመግባቱ በፊት ጾምን ለመቀበል ሲሰናዱ የሚቆዩበት ሰሞን ማለት ነው ቅበላ ሙሽራው ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት አስቀድሞ እንደሚገባ ኾኖ ለመቀበል የመዘጋጃ ሰሞን ማለት ነው።

የምንቀበለው ሙሽራው #ዐቢይ_ጾም ነው ክርስቶስ ከእኛ ጋር እኛም ከክርስቶስ ጋር የምንዋሐድበት ፤ ክርስቶስ ከእኛ ጋር የሚያድርበት በልዩ ሁኔታ የነፍስ ተድላ ደስታ የሚደረግበት የምህላው ፣ የጸሎቱ ፣ የስግደቱ ገበታ የሚዘረጋበት ሰማያውያን መላእክት ሳይቀሩ የሚታደሙበት ነፍሳችን የምትሞሽርበት ታላቁን ዐቢይ ጾምን ለመቀበል የምናደርገው ዝግጅት ነው።

ስለዚህ ዝግጅቱ ሙሽራውንና የሙሽራውን ሥርዓት ለመቀበል ነቅቶ ፣ ተግቶ መቆየት ፣ መዘጋጀት በኋላም መቀበል ነው በአጠቃላይ ቅበላ ሲባል ጾሙን ጸሎቱን ፣ ሱባኤውን ለመቀበል የምንዘጋጅበት ሳምንት ማለት ነው፡፡

የቅበላ ትርጓሜው እንዲህ እያለ ነገር ግን ዛሬ እንደሚስተዋለው የጾምን ወራት አስታኮ የሚታይ ወከባና ጫጫታ ፣ ግርግታ ፣ ጭፈራውን ፣ በወረፋ በልቶና ጠጥቶ መስከሩ ፣ ማንን ለመቀበል ነው ? መቼም ጮማ እየቆረጡ ጠጅ እየጠጡ ክርስቶስን ለመቀበል ነው የሚል ክርስቲያን ካለ እርሱ እጅግ ሞኝ ነው።

አንዳንድ ጊዜ ካሁን በኋላ ሥጋ እንዳትበሉ በሕይወት ዘመናችሁ ይህ የመጨረሻችሁ ነው የሚል አዋጅ የታወጀ እስኪመስል ድረስ በየሥጋ ቤቱ ለረጅም ስዓታት ለወረፋ ተገትሮ መዋል በእውነት ይህ ቅበላ ሳይሆን ብቀላ ነው ሥጋን ለመበቀል ይመስልብናል።

በጾም ጊዜ የማይቀሩ ተግባራት አሉ እነዚህም ጸሎት ፣ ስግደትና ምጽዋት ናቸው ሰውነት እንደ ልብ ቆሞ እንዲጸልይ ጉልበት እንደ ልብ መስገድ እንዲችል በቅበላ ሰሞን የምናደርገው የአመጋገብ ዝግጅት በእጅጉ ይረዳል።

ነገር ግን ጾሙን ስንቀበልም ስንሸኝም የአመጋገባችን ሥርዓት እጅግ የተዛባ ነው ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ « ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን ›› ብሎ ያስጠነቀቀን ሰለዚህ ነው። 1ኛቆሮ፡ 14 ፥ 40

ሐዋርያው እንዳለው « የክርስትና ሕይወት መሠረቱ እግዚአብሔርን የመምሰል ምልክቱ በመጠን በልኬት መኖር ነው » እንዳለ ጾምን ባልተገባ መንገድ መቀበል ራሱ ኀጢአት ነው። አበው ደግሞ « ሹመት በተርታ ሥጋ በገበታ » እንዲሉ ማንኛውም ነገር በሥርዓትና በአግባቡ ሲከናወን ደስ ያሰኛል።

የምናመልከው አምላክ የሥርዓት አምላክ ነውና ከጾምን አይቀር እንደሚገባና እንደ ሥርዓቱ አፍአዊና ውሳጣዊ ዝግጅት ማለትም አካላዊ ፣ መንፈሳዊና ሥነ ልቡናዊ ዝግጅት በማድረግ በምክረ ካህን በመታገዝ ጾሙን ልንቀበል ይገባል።

በአትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ትውፊት መሠረት ሰንበታት ፣ አጽዋማትና በዓላት ከዋዜማው ጀምሮ በጸሎት ፣ በመዝሙር በትምህርትና ወዘተ ልዩ አቀባበል ይደረግላቸዋል።

ቅበላ በተለይ የነነዌ ጾም እንዳለቀ እስከ ዐቢይ ጾም ዋዜማ ድረስ ያለው ሰሞን ሲሆን መናንንያን ፣ ካህናትና ምእመናን ጾሙን ለመቀበል የተለያዩ ዝግጅቶች ያደረጋሉ ጾሙን በንጹሕ ኅሊና ለመጀመር ከመምህረ ንስሐቸው ጋር ይወያያሉ ፤ ምክርና ኅዝናት ይቀበላሉ ፤ የበደሉ ማሩኝታ የተጣሉም ይቅርታ ይጠይቃሉ ። ‹‹ ኀጢአትህን ለማመን ለመናገር አትፍራ ›› እንዳለ ሲራክ 3፥18

ይኽውም በጾሙ ወራት ልናያቸውና ልንሰማቸው ከማይገቡ ሥጋውያት ተግባራት ለመራቅ የሚያስችል የሥነ ልቡና ግንባታ የምናደርግባት ሰሞን ነው ለምሳሌ ሥጋዊ ፊልሞችን ዋዛ ፈዛዛ ያሉባቸው ተውኔቶችን ፤ ድራማዎችን የፖለቲካ ዲስኩሮችንና ወዘተ ከማየት መቆጠብ።

ሥጋውያት መጻሕፍትን ከማንበብ መከልከል በአንጻሩ ደግሞ ምኅላዎችን መሳተፍ ፣ ስብከቶችን ማዳመጥ ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ እነኝህን ለማድረግ ኅሊናን ማዘጋጀት ይገባል።

ሌሊቱን ለሰዓታት ለኪዳን ፣ ቀኑን ለቅዳሴ ፣ ማታውን ለሠርክ ጸሎት ለማዋል ማቀድና እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መተግበር ይገባል ዛሬ ዛሬ ግን ቅበላ ሲባል በአብዛኛው አዕምሮ የሚከሠተው ከሰባው አርዶና አወራርዶ አሊያም ልኳንዳ ቤት ተሰልፎና ታድሞ ፣ጥሉላት ምግቦችን በዓይነት አሰልፎ ፣ ጠጅ ( አልኮል ) ተጎንጭቶ ፣ ከመጠን ያለፈ ደስታ ፈጥሮ ጾሙን መቀበል ሆኗል።

ቅዱስ ጴጥሮስም በመልእክቱ «በመጠን ኑሩ ንቁም ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሣ አንበሳ ይዞራልና ›› እንዳለው ከመጠን ያለፈ ማንኛውም ድርጊት ለፈተና ብሎም በዲያብሎስ ሊያስማርከን ይችላል 1ኛጴጥ 5፥8 ስለዚህ ታላቁን ጾም ለመቀበል ለአንድ ክርስቲያን መንፈሳዊ ዝግጅት በእጅጉ ያስፈልጋል፡፡

#እግዚአብሔር_ጾሙን_በሰላም_አስጀምሮ_እንዲያስፈጽመን_ቅዱስ_ፈቃዱ_ይሁንልን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

18 Feb, 07:07


#ቅዱስ_ያሬድ_ካህን_ማኅሌታይ

#ቅዱስ_ያሬድ ለነፍስ ለሥጋ በሰማይ ለሚጠብቀን ሕይወታችን ሆነ በምድር ላለው ሕይወታችን የሚሆን ቁስለ ነፍስን የሚያክም አጥንትን የሚያለመልም ድንቅ ድርሰቶችን ያበርከተልን ኢትዮጵያዊ ሊቅ ነው ፡፡

ወር በገባ በ11 የቤተክርስቲያን ብርሃኗ እንዲሁም ሙሉ አካሏ የሆነው የሱራፊል አምሳያ ማኅሌታይ ቅዱስ ያሬድ ወርኀዊ መታሰቢያው ነው ኢትዮጵያን
ከቅዱሳን መላእክት ጋር በምስጋና አንድ ያደረገን ታላቅ ባለውለታችን ነው፡፡

ሰውን ብቻ ያይደለ ዓባይን በጥዑም ዜማው ቀጥ አድርጎ ያቆመ፡፡ 24ቱ ካህናተ ሰማይ ያመሰገኑት ምስጉ ነው፡፡

#ቅዱስ_ያሬድ_ሆይ

የእመቤታችን ጽዮን ታቦትን እንዴት አደርሽ የሚሉና የአምላክ ስምን ለሚያመሰግኑ ከንፈሮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡

ከብርሌ ነጭ ለሆኑና ምስል ለሌላቸው ጥርሶችህ ሰላምታ ይገባል፡፡

የምስጋናን ሽታ ለተቀበለ እስትንፋስህ ሰላምታ ይገባዋል፡፡

በሱባዔ እየፆመ ውኀ ለማይጠጣ ጉሮሮህ ሰላምታ ይገባል፡፡

የብርሃን ልብስን ለተሸለመ ጫንቃህ ሰላምታ ይገባል፡፡

ጥበብን ላበዛ ልብህ ሰላምታ ይገባል፤ ዳግመኛም ለኩላሊትህ ሰላምታ ይገባል፡፡

ከጌታ ክርስቶስ ፊት ለሰገዱ ጉልበቶችህ ሰላምታ ይገባል፡፡

የማኅሌትን መዝሙር ለጻፉ ጣቶችህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ከበረዶ ጋር አንድ ለሆኑ ነጫጭ ጥፍሮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡

በእንቅልፍ ጊዜ ለማይተኛ ጎንህ ሰላምታ ይገባል፡፡ የዚህን ዓለም መብል ላልተሸከመ ሆድህም ሰላምታ ይገባል፡፡

ጥበብን ላበዛ ልብህ ሰላምታ ይገባል፡፡

ከንቱ ነገርን ለማያስብ አዕምሮህ ሰላምታ ይጠባል ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ እሳት ለተቃጠለ አንጀትህም ሰላምታ ይገባል፡፡

የተመረጠ ዛፍን ለመሰለ ቁመትህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ላማረ መልክህም ዳግመኛ ሰላምታ ይገባል፡፡

በጎ ሥርዓት ለመመልከት እንደ ጠላ ለሚያስደስቱ አይኖችህ ሰላምታ ይገባል፡፡

የካህናት አለቃ ያሬድ ሆይ ዓለም ወደ ክፉ ወጥመድ እንዳትወስደኝ ላንተ የገባ ትምህርትን እማር ዘንድ አድለኝ፡፡

የቅዱስ ያሬድ አምላክ ሆይ ከሥጋና ከነፍስ መከራ ፈጽመህ አድነኝ፡፡

#መልክዐ_ቅዱስ_ያሬድ

#ከቅዱስ_ያሬድ_ረድኤት_በረከትን_ያሳትፈን_አሜን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

17 Feb, 08:45


ይኽንን የወንጌል ክፍል ሳስብ ሁሌም በዚህ ድንቅ ጽሑፍ መጨረሻ ላይ የሰፈረችዉ ሐረግ ትገርመኛለች "ግንኮ ውኀ አሰጠችሁም" እና ብዙ ነገሮችን አይበታለሁ ግን ሁለት ዕይታዎቼን ላንሳ ከትልቅ ይቅርታ ጋር

፩, እግዚአብሔር ለኛ ያላደረገልን ነገር ምን አለ? እኛስ ለእግዚአብሔር ያደረግንለት ነገር ምን አለ? ብዬ እጠይቃለሁ በእርግጥም እግዚአብሔር ለኛ ያላደረገዉ ነገር የለም ሰዎች በነገሮች የማንጠግብ የማንረካ ሆነን እንጂ ዕለት ዕለት በየሰዓቱ እና በየደቂቃዉ እግዚአብሔር ብዙ ነገርን አድርጎልናል ያደርግልናልም.........ብዙ ልል አልኩና ተውኩት ግን እኛስ ምን አድርገንለታል ብዙ ጊዜ እኛ ለእግዚአብሔር ምንም ማድረግ እንደማንችል እንናገራለን እውነት ከኛ አቅመ ቢስነት እና ከእግዚአብሔር ሁሉን ቻይነት አንጻር ካየነዉ ምንም ልናደርግለት አንችል ይሆናል ነገር ግን በማቴዎስ በኩል እንደነገረን ለእያንዳንዳችን አትርፈን እናሳየዉ እንመልስለት ዘንድ ከእርሱ ለኛ የተሰጠን እና ለርሱ መልሰን የምንሰጠዉ ነገር አለን ያ እንደ አቅማችን የሚለካ ቢሆንም ግን እኛም ለእግዚአብሔር የምንሰጠዉ የምናደርግለት ነገር እንዳለ የሚያሳይ ነው ያዉ የመጀመርያዉ ተጠቃሚዎች እኛዉ ብንሆንም ቅሉ እና ይኽንን ማድረግ አለመቻላችን ያሳዝነኛል ለእግዚአብሔር አንዳች ነገር አድርጎ ከመሸለም ይልቅ በማይረባ በማይጠቅም ግሳንግስ ጉዳዮች ተጠምደን ስንዳክር የምንገኝ መሆናችን ያስገርመኛል የጠየቀንን ውኀ እንኳን ልንሰጠዉ አልቻልንም ሉቃስ እንደነገረን ምንም ባላደርግ ባስቀይመዉም ባሳዝነዉም ልጁ ነኝ አይጨክንብኝም ወደ አባቴ ቤት ሄጄ እንደባርያ ልኑር ልበለዉ ብለን የምንመለስበት የተሰበረ ልብ እንኳን የለንም ይኽ ያስገርመኛል።

፪, እኛ አገልጋዮችን ያስታውሰኛል በተለይ በዘመናችን "በከንቱ ዘነሳይክሙ ሀቡ በከንቱ" የተባለዉን የዘነጋን ጥቅም አሳዳጆችን ያስታውሰኛል ወንጌልን ለመስበክ የምንደራደር ሰነፎችን ያስታውሰኛል ኑ ሕዝባችን ወንጌልን መሰበክ ይፈልጋልና አስተምሩልን ስንል ቤተ ክርስቲያኗ ስንት ትከፍላለች፤ መኪና መጥቶ ካልወሰደኝ አልመጣም፤ ባለ ፬ ኮከብ ሆቴል ካልተያዘልኝ፤ እራት ቁርጥ ካልቀረበልኝ.....የምንል ከርሶሙ አምላኮሙ የተባለብን አገልጋዮች ከላይ እስከታች ያለነዉን ያሳስበኛል በዚህም በጣም አዝናለሁ!

ቃለ ሕይወትን ያሰማልን መምህርዬ እንደዉ ውስጤ የሚመላለስን ጉዳይ ስለነካኝ ነው ይቅርታ ይደረግልኝ በድጋሚ 🙏

#መምህር_ሳዶር_በኮመንት_ያሠፈርኩት_ነዉ_ይጠቅማል_ብዬ_አጋራኋችሁ!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

17 Feb, 08:35


#አንዳንድ_የድካም_ንግግሮችን_ስለ_መዝለል!

ዮሐ 4፥4 የዘመነ ቅበላ የዕለተ ሰንበት ወንጌል በኑሯችን ሁሉ እንዴት መራመድ እንዳለብን ጌታችን ያቺን ሳምራዊት ሴት ካናገረበትና ካስተማረበት መንገድ በጣም ብዙ የምንማረው ነገር አለ

ጌታችን ሴቷ ከመምጣቷ በፊት ቀድሟት ሄዶ ነው ምንጩ ዳር የተገኘው እንኳን ወደ እኛ መጥተው ለሚማሩት ይቅርና ወደ ችግረኞች ሄደን ማስተማር እንዳለብን ያሳያል የምንሄደውም በምቾት ሳይሆን የፀሐዩ ሐሩር በበረታበትና በቀትር ተጠምተንና ደክመን መሆን እንዳለበት ያሳያል ወደኪሞ እግዚእ ኢየሱስ በሐዊረ ፍኖት ይላል።

ጌታ ውኃ አጠጪኝ ሲላት ለተጠማ ሰው ውኃ ከማጠጣት ይልቅ የዋለ ያደረ የሕዝብ ጥያቄ እያነሳች በጥማቱ ላይ አደከመችው እንጂ ልታጠጣው አልወደደችም አንዳንዴ ሰዎች ከምን የተነሣና በምን ምክንያት ከንግግራችንና ከሐሳባችን እንደሚርቁ መረዳትና ሕመማቸውን ማወቅ አለብን ከሰው ምላስና ንግግር ይልቅ የቀኑ ሐሩር ይሻለኛል ብላ ወደ ወንዝ የመጣች ሴት ናት ብዙ ሆድ የባሳት ሴት ናት ምንም ብትናገር ይገባታል እግዚአብሔር በእርሷ ብቻ የጨከነ እስኪመስላት ድረስ ከአምስት ባሎች ጋር የነበራት ነገር የተበላሸ ነው በምድር ላይ ለሰዎች መሳለቂያ ሆና የተፈጠረች እስኪመስላት ድረስ ሰዎች የሚጠቋቆሙት በእርሷ ነው ይህ መገለሏ ሳያንስ ደግሞ እንደ ሕዝብ ደግሞ እስራኤልና ሰማርያ ተብለው መከፋፈላቸው አንዱ አንዱን ማቃለሉምና መጸየፉ ያሳስባት ኖሯል
በማምለኪያ ቦታቸው ሳይቀር ተከፋፍለው እነዚያ በኢየሩሳሌም ብቻ እነርሱም በዚህ ተራራ ብቻ የሚል አቋም መያዛቸውም እንደ አቅሟ የሃይማኖት ጥያቄ ነበራትና ጌታ በትምህርት ሲያሳድጋት ይህን ሁሉ አጀንዳ ቀስ በቀስ እያነሣች ጥያቄዋን አቅርባለች

ስለዚህ ጌታ የልቧን ቁስል የአእምሯዋን መጎዳት ሁሉ ተረድቶ ውኃ አጠጪኝ ሲላት ውኃ ከመስጠት ይልቅ በደኅና ጊዜ ትጸየፉን የለም ወይ? እንዴት ከእኔ ሳምራዊቷ ሴት ለምን ውኃ ትለምናለህ አለችው? ለተጠማ ሰው የውኃ መቅጃ ይዞ ነገር መቅዳትኮ ያማል ጌታ ግን ውስጣዊ ሕመሟን ስለሚያውቅ ሊያክማትና ስውር ጥማቷን ሊያበርድላት ማስተማር ያዘ ሕመሟን ያውቃልና አልፈረደባትም ኒቆዲሞስን አንተ የአይሁድ መምህር ሆነህ ሳለህ ይህንን አታውቅምን እያለ የገሠጸው ጌታ ይህችን ሴት ግን በልኳና በሕመሟ ልክ ማከም ያዘ ሰዎች የሚሰጣቸው መድኃኒት በእነርሱ ጥንካሬና ድካም ልክ ነውና መድኃኒቱን መቋቋም የማይችሉም ስለሚኖሩ ነው።

እርሱም የሚለምንሽ ማን እንደሆነስ የእግዚአብሔርን ስጦታ ብታውቂ ብሎ ማንነቱንና ምንነቱን በምሥጢር ነገራት እንኳን መቅጃሽን ልጸየፈው ይቅርና ከሕዝብና ከአሕዛብ ተወልጄ የመጣሁ የሕይወት ስጦታ ነኝ እያላት ነው

መቅጃ የለህም ጉድጓዱ ጥልቅ ነው ብላ ሌላ ክርክር አነሣች ለጊዜው የሚጸየፏቸው አይሁድ ስለሆኑ እርሱ እስካልተጠየፋትና እስካልናቃት ድረስ ውኃ መስጠት ነበረባት
እርሱ ግን በሰለቻት መንገድ ሊያስተምራት እኔ ከምሰጠው ውኃ የሚጠጣ አይጠማም አላት ይህንን ሲላት በእየ ጊዜው ፀሐይ እየቀጠቀጣት ብቻዋን ወደ ምንጩ የምትመላለስበት የሰለቸ የድግግሞሽ ሕይወቷ ታያትና እባክህ ይህንን ውኃ ስጠኝና ከመመላለስ ገላግለኝ አለችው
ይገርማል የራበው ሰው እግዚአብሔርን የሚያየው በእንጀራ ሒሳብ ነው እንደሚባለው ሁሉ የዚህች ሴት የሕይወት ውኃ ማለት አንዴ ተጠጥቶ ወደ ወንዝ አለመመላለስ ነበር ጌታም ባልሽን ጠርተሽ ነይ በማለት በንስሐ ወደ ሥርዓተ ቁርባን ስንቀርብ ባል ሚስትን ሚስትም ባሏን ይዛ ለመቅረብ መጣር እንዳለባቸው ሲያስረዳ የሕይወት ውኃን ለመጠጣት ባልሽን ጥሪ አላት በዚህ ንግግሩም ወደ ትክክለኛ ሕይወቷ ገባ ገና እንዳገኛትና ውኃ አጠጪኝ ሲላት አምስት ባሎች እንደሸኘች ቢናገራት ኖሮ በምሬትና ተስፋ በመቁረጥ እርሱንም በሸሸችው ነበርና እያባበለ አስተማራት
ብዙ ሐኪሞች በመልካም መንገድ ያክሙ ይሆናል ጌታ ይህችን ሴት ያከመበትና ቁስሏን የጠረገበት መንገድ ግን እጅግ ይደንቃል ለካ ሳምራዊት ሴት መሆኔን ብቻ ሳይሆን ይህንን ሁሉ ጉዴንና ነውሬንም እያወቀ ነው ውኃ የለመነኝ ብላ እንድትደነቅም አድርጓታል

አምስት ባሎች ነበሩሽ ብሎ ማንነቷን ሲነግራት የእኔን ሕይወት ተወው ለጨዋታም ለአጀንዳም አይመችም ይልቁንስ ነቢይ ትመስለኛለህ ስለዚህ ሃይማኖታዊ ጥያቄ ላቅርብ ብላ ከእንስራ ጀርባ የሃይማኖት አጀንዳ መዘዘች ጌታም ይህንንም በሚገባት መንገድ አስረዳት እርሷ ግን ምሥጢሩ ስለረቀቀባት የቀረውን ደግሞ መሲሑ ሲመጣ ሁሉን ይነግረናል ብላ በነቢያት ተስፋ የምትኖር ሴት መሆኗን ተናገረች በዚህ ጊዜ ጌታ ስብከቱን ጨረሰና የምትይው እኮ እኔ ነኝ አላት ይደንቃል በመዋዕለ ሥጋዌው ጌታ እራሱን የገለጠው ለሁለት ሰዎች ሲሆን አንዷ ይህች እድለኛ ሴት ናት

ጌታችንም እንዲህ ተጠምቶና ደክሞ አልቀረም ይህንን ሁሉ ካየች በኋላ ከሰው ተደብቃ በቀትር የመጣች ሴት ሰው ምን ይለኛል ሳትል ወደ መንደር ገብታ ሕዝብ መሰብሰብ ጀመረች ብዙ ሰው አስከትላ መጣች ከሰው ተደብቃ የጨለማ ሕይወት የምትመራ ሴት ለብዙ ሰዎች ብርሃን ሆና ተገኘች እንሥራና ውኃ አጀንዳዋ ላይሆን ለመጨረሻ ጊዜ ጥላው ሄደች ለብዙ ዘመን ሰዎች የጫኑባት ነውሯና ፍርሐቷ የተወገደው በጥቂት ደቂቃዎች የጌታ ስብከት ነበር ዛሬም እኛ የተስፋ መቁረጥ እና የብሶት እንሥራ የተሸከሙ ሰዎችን በንግግራቸው ልክ ከመናገርና በድካማቸው ልክ ከምንፈርድ ይልቅ ብሶታቸውን የምንጠግንበትና የምናክምበትን ጥበብ አምላከ ቅዱሳን ያድለን።

#ግን_እኮ_ውኃ_አላጠጣችውም
#መጋቤ_ሐዲስ_ዘለዓለም

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

15 Feb, 06:15


#ዓይኖቼ_ማዳንህን_አይተዋልና...

በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየዓመቱ #የካቲት_8 ቀን ከሚከበሩ በዓላት መካከል የጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ መቅደስ መግባት፣ የነቢዩ ስምዖን ልደት (መታደስ) እና የነቢዪት ሐና ዕረፍት በስፋት ይነገራል ፡፡

ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደ በስምንተኛው ቀን (ጥር 6 ቀን) በኦሪቱ ሕግ መሠረት ሥርዓተ ግዝረትን ፈጽሟል በተወለደ በዐርባኛ ቀኑ (የካቲት 8 ቀን) ደግሞ ወደ ቤተ መቅደስ ገብቷል (ጌታችንመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተወለደበት ከታኅሣሥ 29 ቀን ጀምረን ስንቈጥር የካቲት 8 ዐርባኛው ቀን ነው ፡፡)

በኦሪቱ ሥርዓትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እና ጠባቂዋ ጻድቁ ዮሴፍ ለመሥዋዕት የሚቀርቡ እንስሳትን ይዘው ጌታችንን በዚህች ዕለት ወደ ቤተ መቅደስ ወሰዱት ፡፡

በዚያም ክርስቶስ ኢየሱስን ሳያይ እንደማይሞት የተነገረው ስምዖን የሚባል ሰው ነበር ይህስ እንደምንነው ? ቢሉ የኦሪት መጻሕፍትን ከዕብራይስጥ ወደ ጽርዕ (ግሪክ) ቋንቋ እንዲተረጕሙ ከታዘዙ ሰብዓ ሰዎች (ሊቃናት) መካከል አንዱ ነቢዩ ስምዖን ነበር ።

ይህ ነቢይ ትንቢተ ኢሳይያስ ደረሰውና እየተረጐመ ሳለ ‹‹እነሆ ድንግል ትፀንሳለች፤ ወንድ ልጅንም ትወልዳለች ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች » ከሚለው ኀይለ ቃል በደረሰ ጊዜ በቀጥታ ቢተረጕመው ንጉሡ እንደማይቀበለው በማሰቡ፤ እርሱም ‹‹ይህ እንዴት ሊኾን ይችላል?›› ብሎ በመጠራጠሩ ‹‹ድንግል›› የሚለውን ቃል ‹‹ወለት›› (ሴት ልጅ) ብሎ ተረጐመው፡፡

ተኝቶ በነቃ ጊዜም ‹‹ወለት›› የሚለው ቃል ተፍቆ ‹‹ድንግል›› ተብሎ ተጽፎ አገኘና እርሱም ‹‹ድንግል››ን ፍቆ ‹‹ወለት›› ብሎ ይጽፋል ዳግመኛም ለሁለተኛና ጊዜ ተኝቶ ሲነቃ ቃሉ እንደ ነበረ ኾኖ ያገኘዋል ፡፡

ለሦስተኛ ጊዜ ቃሉን እፍቃለሁ ሲልም የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦ ‹‹የተጠራጠርኸውን፣ ከድንግል የሚወለደው ክርስቶስን እስከምታየውና እስከምትታቀፈው ድረስ ሞትን አትቀምስም፤›› ብሎታል፡፡

‹‹መሲሑን ሳታይ አትሞት›› የተባለው ነቢዩ ስምዖን አርጅቶ ከአልጋ ተጣብቆ ለሦስት መቶ ዓመታት ያህል ከኖረ በኋላ ትንቢቱ ተፈጽሞ፣ ዘመኑ ደርሶ ክርስቶስ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በተወለደ በዐርባኛው ቀን ወደ ቤተ መቅደስ እስከ በገባበት ዕለት መንፈስ ቅዱስ አነሳሥቶ ወደ ምኵራብ ወሰደው፡፡

በዚያም ጌታችንን ከእመቤታችን ተቀብሎ ለመታቀፍ ታድሏል። ‹‹የምትጠብቀው ሕፃን ይህ ነው›› ብሎ እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በነገረው ጊዜም ታውረው የነበሩ ዓይኖቹ ተገልጠዋል፤ ሰውነቱም ታደሷል፡፡

ነቢዩም የእግዚአብሔርን ማዳን በዓይኑ በማየቱ፣ ከደዌው በመፈወሱ እና ከእርጅናው በመታደሱ በአጠቃላይ በተደረገለት ድንቅ ተአምር ዅሉ በመደሰቱ እግዚአብሔርን አመስግኗል፡፡

‹‹አቤቱ ባሪያህን ዛሬ አሰናብተኝ፤ ዓይኖቼ ማዳንህን አይተዋልና ፤ » በሚለው ትንቢታዊ መዝሙሩም ‹‹የእግዚአብሔርን ማዳን በዓይኔ ስላየሁ እንግዲህስ ልረፍ›› በማለት ሞቱን ተማጽኗል፡፡

በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶም የክርስቶስን የዓለም ቤዛነትና ክርስቶስ በሥጋው በሚቀበለው መከራ እመቤታችን መራራ ኀዘን እንደሚደርስባት፤ እንደዚሁም ጌታችን ለሚያምኑበት ድኅነትን፣ ለሚክዱት ደግሞ ሞትን የሚያመጣ አምላክ እንደ ኾነ የሚያስገነዝብ ትንቢት ተናግሯል፡፡

የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት ለነቢዩ ስምዖን የተደረገለትን ታላቅ ሥራ ሲያደንቁ እንዲህ ይገልጹታል፤ ‹‹የማኅሌት መዝሙርን በማዘጋጀት እያከበርሁትና እያደነቅሁት ከሱራፌል ክብር ለሚበልጠው ለስምዖን ክብር ሰላም እላለሁ፡፡ እርሱ መለኮትን በእጁ ታቅፏል፤ እሳቱንም ዳሷልና እቅፎቹን እጅ እነሳለሁ፤ እጆቹንም እስማለሁ፤ ››

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

15 Feb, 06:10


#ወዴት_አለህ?

የሕጻንነት ወግ መቼም ብዙ ነው ፤ በመዝገብ ቢሠፍር ግን የጥፋቱ ይበልጡን ቦታ እንደሚይዝ አያጠራጥርም። አዲስ ነገር ለማወቅ በመፈለግና አታድርጉ የተባሉትን ነገር ለማድረግ በመሻት ውስጥ የእናቶቻችንን አንጀት ያቆሰልንባቸው ጊዜያት ይበዛሉ።

በምሳሌ "እናት ትረገጣለች እንደ መሬት" ይባላል ፤ የፍቅሯ ጽናት ጥያቄ ውስጥ አይገባምና ለልጇ ስትል የምትከፍለውን ዋጋ ለማሳየት። ታዲያ ልጇ መስመር እንዳይስትና እንዳይበላሽ ቅጣቷም ቀላል የሚባል አይደለም። አጥፍተን ስትጠራን ልትመርቀን እንደማይኾን አይሠወረንም ፤ 'ና ልጄ ምንም አልልህም' የሚለው ጥሪዋ ውስጥ ቃጠሎው የማያባራ ቁንጥጫ አልያም ሕመሙ የማይታገስ ዱላ እንዳለ አስተውለን እግሬ አውጪኝ ለማለታችን ቊጥር አናስቀምጥም።

የእናታችን ጥሪ 'ና' የሚል ይኹን እንጂ ጥፋት ሠርተንና የማይደረግ ፈጽመን 'ወዴት አለህ?' የሚል አይደለም። ለነገሩ ከፊቷ የምታየው ልጇ እንዳይሸሽ ብላ 'ና' ብትል ድንቅ አይደለም ፤ ተሸሽጎም እንደው 'ወዴት አለህ' ብትል ሥጋ ለባሽ አላዋቂ ናትና ዕጹብ አያስብልም።

'እናት' ከተባለች ምድር 'አባት' ከተባለ እግዚአብሔር ተገኝቶ 'እጓለ እመሕያው' የተባለ አዳም "አትብላ!" የተባለውን ዕጽ በበላ ጊዜ ወደእርሱ የመጣው ድምጽ ምን የሚል ነበር? "አዳም አዳም ወዴት አለህ?" (ዘፍ ፫÷፱) ይህ ድምጽ ኹሉን የሚያውቅ የእግዚአብሔር ድምጽ ነው! ይህ ድምጽ ዓለምን በመዳፉ የያዘ ኹሉም ፈጥሮ የሚገዛ የእግዚአብሔር ድምጽ ነው!

የበደለውን ይቅር ሊል ፤ በእርሱ የኾነውን ሞት በእኔ ይኹን በማለት ሊቀበል ፤ ተበድሎ ሊክስ 'ወዴት አለህ?' የሚል ከእግዚአብሔር በቀር ከወዴት ይገኝ ይኾን?

ከአዋቂነት የተራቆተውን አላዋቂ ሥጋ በኋላ ዘመን ተዋሕጄ አድንሃለኹ ሲለው 'ወዴት አለህ?' በማለት ቢናገረውም ፤ እንደምን ባለ አነዋወር አለህ? በሰጠሁህ ክብር ወይስ በኃሣር? በውድቀት ወይስ በተመኘኸው አምላክነት? ብሎ መጠየቁን የዘፍጥረት ትርጓሜ ይናገራል።

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅም "ለበደለው ታላቅ በደል መልስ እንዳይሰጥ ማድረግ ፤ ላጠፋውም ጥፋት በአንድ ጊዜ መቅጣት ሲቻለው ተጸጽቶ መልስ ይሰጥ ዘንድ ዕድሉን ሰጠው ትዕግስቱንም አሳየው።" ሲል ይናገራል።

አዳም ተራቁቶ የሠራውን ለመናገር ቢፈራ ፤ እግዚአብሔር ግን 'ወዴት አለህ?' ብሎ ልጁ እንዲያወራ የአባትነት ጥሪን ያቀርባል ፤ የምሕረቱ ብዛት የፍቅሩም ጥልቀት የሚመረመር አይደለምና!

የጸጸት ልብ ባይኖረንም ፤ በኃጢአታችን የጽድቅ ያህል ብንመካም ፤ ለድፍረታችን ጥግ አጥተን ለበደላችን ጥቅስ ብናበጃጅም ዛሬም የምሕረት እጆቹ ያልታጠፉ አምላክ 'ወዴት አለህ?' 'ወዴት አለሽ?' ይላል! በቅጣቱ እንዳንፈራውና በወደቅን ጊዜ ምሕረቱን እንድናስብ የፍቅር መዳፎቹ ወደእኛ ይዘረጋሉ! ታዲያ ለዚህ ጥሪ ምላሻችን ምንድር ነው?

አለመበደል የመጀመሪያው ምርጫ! ከወደቁም አምኖ 'ይቅር በለኝ' ማለት ምርጫ የሌለው ምርጫ!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

13 Feb, 16:10


"ወንጌል ስለ ኢየሱስ ብቻ ነው" ያለ ማን ነው?
ተሳስቷል። የፍቅሩና ቤዛነቱ ምስክር የኾኑ ቅዱሳትና ቅዱሳን መታሰቢያቸው በወንጌል እንዲጻፍ ያዘዘ እርሱ ራሱ ኢየሱስ ነውና።

በዝሙት የኖረች አንዲት ሴት ነበረች ማርያም ዘናይን/ኀጥእት ትባላለች የጌታችን ክርስቶስን የእጁን ተአምራት አላየችም የቃሉን ትምህርት አልሰማችም እንደወትሮዋ በመስታወት ፊት ቆማ ስትኳኳል ውበቷን የሚያጠፋ ሞት ትዝ አላት ይቅርታና ምሕረት ለማግኘት ወደ መሐሪው ጌታ ፈጥና ኼደች በስምዖን ፈሪሳዊ ቤት አገኘችው።

"የረከሰ ነገርን የነካችኹ እጆቼ ሆይ የጌታ ክርስቶስን እግር ትዳስሱ ዘንድ ታደላችኹ።" እያለች የጌታዋን እግር በዕንባ አጠበች ጌታችን ክርስቶስም "እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ አላት"

ደቀ መዛሙርቱንም እንዲህ ሲል አዘዛቸው “እውነት እላችኋለሁ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።” ማቴ፡ 26፥13 በሰላም ሂጂ ያላት ጌታ ዛሬ የካቲት ስድስት ወደ ጻድቃን ከተማ ወሰዳት።

ይኽች ማርያም የአልዐዛር እኅት ማርያም ወይም ማርያም መግደላዊት አይደለችም።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

12 Feb, 14:00


#ኢትዮጵያ_እና_ነነዌ

ነነዌ በመጸሐፍ ቅዱስ ከትንቢተ ናሆም በተጨማሪ ስለርሷ ብቻ የሚገልጽ ዐራት ምእራፍ ያለው ትንቢተ ዮናስ የሚባል ቅዱስ መጸሐፍ የተጻፈላት የገናና ታሪክ ባለቤት የሆነች የንጉሥ መቀመጫ ከተማ ናት ነገር ግን ባንድ ወቅት ነነዌ የክፋት መፍለቂያ የዝሙት መነኻሪያ የሙስና ማእከል የገዳዮች ዋሻ የመተተኞች መከማቻ የምቀኞች ማደሪያ የገዳዮች ዋሻ በመሆን ፈጣሪዋን አሳዘነች በደሏም ወደፈጣሪ ደረሰ።

በውስጧም የነበረው ነቢይ ሰባኪ ዮናስ ይባላል ቢሰብክ ቢያስተምር የሚሰማው በማጣቱ ተስፋ ቆርጦ ተቀመጠ ነገር ግን የእግዚአብሔር ቃል ዮናስን ወደነነዌ ሂዶ እንዲያስተምር ደጋግሞ ነገረው ዮናስም በነገሩ ተከፋ ቦታውን ለቆ ለመሄድ ወሰነ
በመርከብም ተሳፈረ።

ጉዞውም ከእግዚአብሔር ለማምለጥ ነበርና አልተሳካለትም ወደ ላይ ቢወጡ ወደታች ቢወርዱ ወዲያ ወዲህ ቢሉ እርሱ የሌለበት ቦታ የለምና መርከቡ ተናወጠ ማዕበሉም ባሕሩን ያማታው ጀመረ ዮናስ ግን አንቀላፍቷል ዮናስም ከእቅልፉ በነቃ ጊዜ በደሉን አወቀ መርከበኞቹም እጣ ተጣጣሉ እጣውም ለዮናስ ደረሰው ወደ ባሕሩም ተወረወረ ከእግዚአብሔር የታዘዘ ዓሳ አንበሪ ዮናስን ዋጠው ከሦስት ቀንና ሌሊት በኋላ ነነዌ አደረሰው ከየብሱም ላይ ተፋው የእግዚአብሔርም ቃል ወደዮናስ መጣ።

እነሆ ነነዌ እስከ ሦስት ቀን ትጠፋለች በማለት አስተምር አለው። ዮናስም በከተማዋ እየዞረ አስተማረ ሕዝቡም ስብከቱን ሰሙና ከልጅ እስከ አዋቂ እንስሳቱን ጨምሮ ከመብል ከመጠጥ ተከለከሉ ማቅ ለበሱ ወደ አምላካቸው ጮኹ አምርረው አለቀሱ የተላከው መቅሰፍትም ከሰማይ ዝቅ ከምድር ከፍ ብሎ ታየ ረጃጅም ዛፎት በመቅሰፍቱ እሳት ተቃጠሉ የነነዌ እሳትም እንደ ሔዋን ቅጠል በጥሶ ተመለሰ።

ነነዌ ግን ዳግም ልደቷን አከበረች
ከሰዶም ከገሞራ ላትቆጠር ነጻ ወጣች በክፋቷ የመጣባትን መቅሰፍት በጸሎቷ መለሰች ሕዝቡ ሁሉ ባንድ አንብተዋልና እግዚአብሔር ነነዌን አሰባት ቀኝና ግራቸውን ያልለዩ ሕፃናትን ተመለከተ እንስሳቱንም ታደገ።

ዛሬ ዛሬ እኛ ኢትዮጵያውያን እንደ ነነዌ ሰዎች በድለናል ክፋታችን ጥልቅ ነው ሰዎች እርቃናቸውን የሚጨፍሩባት ዝሙት ባደባባይ የነገሠባት ሰው ወደ እንስሳነት የተቀየረባት ግድያ ሰቆቃ ዋይታ የበዛባት ሀገር ሆናለች ኢትዮጵያ ፈጣሪዋን ማስቀየሟ በደሏ ከፍ ማለቱ ከፈጣሪ ዘንድ መድረሱን መዘንጋት የለብንም።

ድኾች አልቅሰዋል ገዳማት ተደፍረዋል ሰዎች ታርደዋል ዝሙት በውስጧ ነግሷል የተጸነሱ ሕፃናት በመድኃኒት የሚበጠበጡ በአምስት ወር የሚጨነገፉ ሁነዋል።

ተወልደው የተጣሉ ታንቀው የተገደሉ ብዙዎች ናቼው በደላችን ከነነዌ በላይ ነው።

ጸሎታችን ጩኸታችን ግን ከነነዌ ሰዎች ጩኸት ያነሰ የደከመ ነው።

ስለዚህ ከነነዌ ሰዎች ተምረን በጋራ ልንጾም
ልንጸልይ ልናነባ ይገባናል።

እኛ እንደነነዌ ሰዎች የሃይማኖት አባቶቻችን እንደዮናስ ቆርጠን ልንነሳ ልንለወጥ ያስፈልገናል።

ያኔ ያንጃበበው ጦርነት ያንጃበበው መከፋፈል መበላላት መገዳደል መጨካካከን ባየር ላይ ይቀራል።

ሀገራችንም የጸነሱ የሚወልዱባት ያጩ የሚያገቡባት ሽማግሌዎች የሚጸልዩባት ሃይማኖት ያልጠፋባት ትሆን ዘንድ በጋራ እንጸልይ እናንባ።

እስካሁን ሰዓት የኖርነውም እንደኛ በደል ሳይሆን ዕቀብ ሕዝባ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ እያሉ የሚጸልዩ ጤዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው ሰለ ሀገር የሚያነቡ አባቶች ስላሉን ደግሞም የቃል ኪዳን ሀገር ስለሆነች የቅዱሳን ምልጃ ስላልተለየን ከሁሉም የበለጠው የፈጣሪ ቸርነት ስለጠበቀን ነው።

የቅዱሳን ምልጃ አሁንም አይለየን የፈጣሪ ቼርነት ከተቃጣ መቅሰፍት ይሰውረን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

10 Feb, 05:18


ጾ መ : ነ ነ ዌ
ጣ ዕ ም ፡ የ ሌ ለ ው ፡ ስ ብ ከ ት

ወደ ከተማችን አንድ ሰባኪ ሊሰብክ መጣ ፣ የመጣው ለመስበክ ፈልጎ አልነበረም እኛን ለማዳን ጉጉት አድሮበት ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ሊያሰማን ጓጉቶ አልነበረም በግድ ተገፍትሮ ፣ ተተፍቶ ፣ ተወርውሮ የመጣ ዓይነት ሰው ነበር ፡፡

ወደ መሃል ከተማም አልገባም የከተማችን አንድ ሦስተኛውን ብቻ ከተጓዘ በኋላ ስብከቱን ጀመረ የሰበከው ስብከት ሰላምታ የለውም ፣ መግቢያ የለውም ፣ መውጫም የለውም ፣ ማጽናኛም የለውም ‹ ንስሓ ግቡ › የሚል አዋጅ የለውም በጩኸት የተናገረው አንድ አስደንጋጭ ዐረፍተ ነገር ብቻ ነበር ‹‹ በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች !! ›› ከነነዌ ነዋሪዎች አንዱ የነነዌን ታሪክ ቢጽፈው የሚጽፈው እንዲህ ነበር ፡፡

የነነዌ ሰዎች እግዚአብሔርን የማያውቁ አሕዛብ ናቸው ዮናስ ደግሞ እነርሱ የማያውቁትን አምላክ የሚያመልክ ነቢይ ነው ዮናስ ወደ እነርሱ የመጣው የማዳን ተልዕኮ ይዞ አልነበረም ፡፡

ወደ አሕዛብ መላኩ አላስደሰተውም ዮናስ ወደ ነነዌ የመጣው እንደ ሌላ ሰባኪ በየትኛውም ትራንስፖርት ተጉዞ ሳይሆን በዓሣ አንበሪ ወደ ነነዌ ተተፍቶ ነው ፡፡

የተተፋ ሰባኪ እንዴት ደስ ብሎት ይሰብካል ? እንኳን ስብከት ይቅርና ማንኛውም ሥራ ያለ ፍላጎት እንዴት ሊሳካ ይችላል ? ዮናስ የነነዌ ሕዝብ እንዲድን ፍላጎትም አልነበረውም እንዲያውም ከመጀመሪያውም ፍርሃቱ ‹ ትጠፋላችሁ › ብሎ ተናግሮ ሳይጠፉ ቢቀሩስ የሚል ነበር ፡፡

ዮናስ ወደ ከተማይቱ ዘልቆ ሲገባም በፍላጎት አልሰበከም ፤ የሰበከው ስብከት ተስፋ የሚያስቆርጥ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ነበር የነነዌ ሰዎች የማያውቁትን አምላክ እንዲያውቁ ዕድል የሚሰጥ ትምህርት አልተሠጣቸውም ፡፡

ዮናስም እንደ ኖኅ ‹ ይኼንን ያህል ዘመን ተሠጥቷችኋል ተመለሱ › ብሎ አልሰበከም መርከብ ሠርቶ ግቡም አላላቸውም በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች › ብሎ ጮኸ ፡፡

የነነዌ ሰዎች ግን ( ማን ነው የሚገለብጣት ? › ለምን ትገለበጣለች ? › ‹ ለመሆኑ አንተ ማን ነህ ? › ( ዝም ብሎ ትገለበጣላችሁ ይባላል ? መጀመሪያ ትምህርት አይቀድምም ? › አላሉም ፡፡

ራሳቸውን እንጂ ሰባኪውንና ስብከቱን ለመገምገም ጊዜ አልነበራቸውም፡ ‹‹ እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ ከታላቁ ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ ››

አንድ ላይ ኃጢአት መሥራት ቀላል ነው ፤ አንድ ላይ ንስሓ መግባት ግን ይከብዳል በሀገር ደረጃ ንስሓ መግባት ግን እጅግ ያስደንቃል የነነዌ ሀገር ህዝቦች ሀገር የምትገለበጥ ከሆነ ሀገር እንቀይር › አላሉም ፤ ራሳቸውን መቀየር እንደሚሻል ተረድተው ነበር ሁሉም እኩል ልቡ ተሰበረ ፤ ሁሉም ማቅ ለበሰ ፡፡

የሰባኪው ስብከት ጣዕም የለውም ብለው አላማረሩም ፣ ‹ ተስፋ የሚሠጥ ስብከት መቼ ሰማን › አላሉም ሰባኪው እያዋዛ አላስተማራቸውም ፣ ምሳሌ አልነገራቸውም ፣ ቅኔ አልተቀኘላቸውም

ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል ‹‹ የተላከላቸው ጨካኝ ሐኪም ነበር የያዘው መድኃኒትም የሚያቃጥል ነበር ፤ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ቃል ተናገራቸው ፤ እነርሱ ግን አቁስሏቸው ተፈወሱ ›› የነነዌ ሰዎች ንስሓ ከላይ እስከታች ነበር ነገሥታቱ ሳይቀር ማቅ ለበሱ ‹‹ ነነዌ ትገለበጣለች ›› ብሎ ሲናገር ንጉሡ ወታደሮች ልኮ ዮናስን ማሰር ይችል ነበር ፡፡ ‹‹ ምን በሀገራችን ላይ ታሟርታለህ ? ›› ብለው_አፉን አላፈኑትም ።

መፍትሔውን ንገረን ያለውም የለም ችግሩ እነርሱ ናቸውና መፍትሔውንም ያውቁታል ስለዚህ ራሳቸውን መውቀስ ወደዱ ሀገሪቱ በአንድ ልብ አለቀሰች።

ንጉሡ ፡- ሰዎችና እንስሶች አንዳች አይቅመሱ ! ብሎ አዋጅ አስነገረ ከቤተ መንግሥት ጾም የሚታወጅባት ነነዌ እንዴት የታደለች ናት ? ‹‹ መኳንንቶችሽ ማልደው የሚበሉ አገር ሆይ ወዮልሽ ›› ተብሎ ከተጻፈ መኳንንቶችዋ የሚጾሙላት ሀገር እንዴት የታደለች ትሆን ? ( መክ . 10 ፡ 16 )

መቼም ሕዝብ ብቻ መጾሙ ነገሥታት ቢበሉ የተለመደ ነው ነገር ግን እየበሉ የሚጾምን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል ? ሲጠጡ እያደሩስ ሲጸልይ የሚያድርን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል ?

ንጉሥሽ ላንቺ ማቅ ለብሶ ያለቀሰልሽ ፣ እንስሳት ሳይቀር የጾሙልሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ ? ሕዝብሽ ጾም ሲታወጅ የማያላግጡ ፣ ‹ እኔ በፈለግሁበት ጊዜ ነው የምጾመው › ብለው የማይመጻደቁ ፣ እንኳን ከቤተ ክህነት ይቅርና ከቤተ መንግሥት የታወጀን ጾም በትሕትና የሚጾሙብሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ ? የዋሐን ሕጻናትን ጡት ከልክለው የፈጣሪን ርኅሩኅ ልብ የሚያስጨንቁ ፣ እንስሳትን ከውኃ ከልክለው ለምህላ የታጠቁ የነነዌ ሰዎች ምንኛ ድንቅ ናቸው ፡፡

ሶርያዊው ቅዱስ ኤፍሬም የቤተ መንግሥቱን ሁኔታ እንዲህ ይሥለዋል ፡፡

‹‹ የነነዌ ንጉሥ ወታደሮቹን ሰብስቦ እንዲህ አላቸውም ፡- ይህ ድል እንደተጎናጸፍንባቸው ውጊያዎቻችን አይደለም ፤ ከባዕድ ሀገር በተሰማው ዜና ኃያላኖቻችን ሳይቀሩ ተብረክርከዋል ፤ አንድ ዕብራዊ መጥቶ በቃሉ አብረከረከን የጀግኖች እናት ነነዌ አንድን ለብቻው የመጣ ደካማ ሰው ቃል ፈርታለች ፡፡ስለዚህ ወገኖቼ ፤ የማይፈርስ አጥር እንገንባ ፤ ይህች አጥር ንስሓ ናት ፤ ሥውር ጦርነት ታውጆብናልና ራሳችንን ሥውር መሣሪያ እናድርግ !! ››

ዮናስ በነነዌ መመለስ ደስ አልተሰኘም ትንቢቱ ስለማይፈጸምለት ብቻ አይደለም ‹‹ የእስራኤል ሽማግሌዎች በሚቀማጠሉባት ሰዓት የነነዌ ሽማግሌዎች ሲያለቅሱ አየ ።

ጽዮን በዝሙት እንደ ሰም ስትቀልጥ ነነዌ ታነባ ነበር ›› እስራኤል ከፈጣሪ በራቁበት ሰዓት አሕዛብ የንስሓ ዕንባ ሲታጠቡ ሲያይ ክብር ከእስራኤል መልቀቁን አይቶ ተከፋ ፡፡

ዮናስ እስከመጨረሻው ሰዓት የነነዌን መጥፋት ይጠባበቅ ነበር ዮናስ ነነዌ የምትገለበጥበትን ቀን ሲቆጥር ነነዌ ደግሞ ኃጢአትዋን ትቆጥር ነበር ፡፡

ዮናስ ስለ ነነዌ እንደ ሙሴ ‹ እነርሱን ከምታጠፋ እኔን አጥፋኝ › አላለም ፤ በተቃራኒው ‹ እነርሱን ካላጠፋህ እኔን አጥፋኝ › እስከማለት ደረሰ በእርግጥም ዮናስ በሽተኛ አክሞ ስለዳነለት የሚበሳጭ ሐኪም ሆነ ፡፡

የነነዌ ሰዎች ግን የሰባኪው ማንነት ፣ የስብከቱ ውበት አልባነት ፣ የአነጋገሩ ለዛ ምክንያት ሳይሆናቸው ተስፋ በማይሰጥ ስብከት ተሰብረው ራሳቸውን አዳኑ ፡፡

ብዙ ስብከት አልፈለጉም ፤ ክፋትን ለመተው እና ይቅር በለን ለማለት የተሰበረ ልብ እንጂ በእውቀት መሞላት አያስፈልግም የኛ ኃጢአታችን ደግሞ ከነነዌ ሰዎች ከበለጠ ቆየ የጋራ ክፋታችንን በጋራ ንስሓ እንጠበው።
ምንጭ ፦ የኤፍራጥስ ወንዝ መጽሐፍ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

08 Feb, 06:02


ማ ር ያ ም : ሆ ይ : ል ደ ት ሽ : ድ ን ቅ : ነ ው !!!

የእመቤታችን ልደት እንደ ማንኛውም ሰው በአጋጣሚ ወይም በሰዎች ተድላ ደስታ እንደሚወለዱት የተወለደች አይደለችም ።

ሰዎች ቢወለዱ ለራሳቸው ጥቅም ነው እመቤታችን ብትወለድ ግን ለዓለም ጥቅም ለአዳም ልጆች ድኅነት ነው ስለዚ ልደቷ ልዩና የሚያስደንቅ ነው ።

ማርያም ሆይ ልደትሽ ድንቅ ነው ሥራሽም ዕፁብ ነው አንደበቷ የሚጣፍጥ በሥራዋ የምትወደድ ከከናፍሮቿ የማር ወለላ የሚፈስባት ስሟን ጠርተን የማንጠግበው የኑሮችን ድባብ የከንፈራችን ጥበብ የድካማችን ምርኩዝ የሕይወታችን መቅረዝ የሆነች እመቤታችን የዓለም መሠረት ጥንተ መድኅኒታችን ናት ።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

07 Feb, 15:17


#ዮሴፍን_የሸጠው_ማን_ነው?

እንደሚታወቀው ዮሴፍ የተሸጠው በወንድሞቹ ነው። ነገር ግን ዮሴፍን ወንድሞቹ ምክንያት ቢሆኑም ወንድሞቹ እንደሚሸጡት ባለመጠርጠሩ ነው።

ይልቁንም ባሪያ ነው ብለው ለምድያማውያን ነጋዴዎች ሊሸጡት፦
" ኑ ለእስማኤላውያን ነጋዴዎች እንሽጠው።"ዘፍ.፴፯፥፳፯ ብለው
ሲዋዋሉበት እኔ ወንድማቸው ነኝ እንጂ የሚሸጥ ባሪያ አይደለሁም የአብርሃም፣የይስሐቅ፣የያዕቆብ ልጅ ነኝ ብሎ ቢናገር ኑሮ ባልተሸጠም ነበር።

ዮሴፍ በዝምታ በመሸጡ ምክንያት እግዚአብሔር የመገፋቱን ዋጋ ባያስቀርበትም በመሸጡ ወንድሞቹ ብቻ አይወቀሱም እርሱም ወንድሞቹ እንደ ጠሉት እያወቀ ባለመጠርጠሩ ሊጠየቅ ይገባዋል።

እኛ ኦርቶዶክሳውያንም የምንመስለው ዮሴፍን ነው። ባለመጠርጠራችን እና ባለመናገራችን ምክንያት ወንድም ዘመድ ካልናቸው ሰዎች የተነሣ ለሥሁት ርዕዮተ ዓለም እና ጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት ልንሸጥ ችለናል።

ዮሴፍ የመናንያን ምሳሌ ሁኖ ለጽድቅ ለትሩፋት ሲል ተሸጠ። እኛ ለዚህ ሁሉ ሥቃይ የተሸጥነው ለምን ብለን ነው?

ከሁሉም መከራ የከፋው ለምድያም ነጋዴዎች መሸጥ ነው። ከነጋዴ ወደ ነጋዴ ያለ ዕረፍት የፈርዖን ባሪያ እስኪሆኑ ድረስ በቃ መሸጥ ነው መሸጥ ነው።

የተሸጠ ሰው ሰው ደግሞ፦ ሀገር የለው፣ዘመድ የለው፣ታሪክ የለው፣መብት የለው፣ዕረፍት የለው፣..ሁለንተናውን የተነጠቀ ምስኪን ነው የሚሆነው። የራሴ የሚለው ምንም ሀብትና ሰውነት የለውም።

"ውረድ ከማማ፣ውጣ ከአውድማ፣ንቀል ከባድማ፣ተሸጥ በሸማ" እየተባለ እንደ ጥሬ ዕቃ ገበያ በደራ ቁጥር ይሻሻጡታል ይለዋወጡታል እንጂ ማንም የሚያከብረው የለም። በመጨረሻም፦"ዮሴፍ ለባርነት ተሸጠ።"መዝ.፻፬፥፲፯ መሸጡን ግን በጽኑ ትጋት በብዙ መከራ ወደ ክብር ቀየረው።

በኢትዮጵያ ያለን ኦርቶዶክሳውያንስ?

የዮሴፍ ወንድሞችስ፦ራእይ የሚያይላቸውን፣ምግብ የሚያደርስላቸውን፣የአጥንት ፍላጭ የሥጋ ቁራጭ የሆነ ወንድማቸውን በ፴ ዲናር ለመሸጥ እንዴት ደፈሩ?

ይሄ ታሪክ እስከ ምጽአት ድረስ እያሳሰበ የሚያስተምረን የመለበሚያ ክፍል ነው።

ዮሴፍን የሸጠው አካል ከውጭ የመጣ አካል የአይደለም። የራሱ ወንድሞቹ ናቸው እንጂ።

ዛሬም ክርስትናችንን እንዲህ በ፴ ዲናር ለግፈኛ መሪዎች እና ለሥሁት ትርክት አሳልፎ የሸጠው ከውስጥ ወንድም ነኝ፣ልጅ ነኝ፣አባት ነኝ፣ሰባኪ ነኝ፣መናኝ ነኝ፣ዲያቆን ነኝ፣ካህን ነኝ፣ጳጳስ ነኝ፣ደጋፊ ነኝ..ሲል የኖረው ነው።

ምን አልባትም እያንዳንዳችን ዮሴፍ-ክርስትናን ለ፴ ዲናር ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ መስየ ልኑር በማለት እየሸጥነው እንዳይሆን ያስፈራል?


#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

07 Feb, 13:12


እንዴት ያለ ድንቅ ማሕበር ለማገልገል ለማዳን የማይታክት።

እነሆ በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት በ“ሃሎ መምህር” እንዲመለስልዎ የሚፈልጉትን ሃይማኖታዊ ጥያቄ በስልክ ቁጥር 0111 55 32 32 በመደዎል ይጠይቁ፡፡ ለጥያቄዎ ማብራሪያ እና መልስ ከመምህራን ያገኛሉ፡፡

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Feb, 04:23


#ቅዱስ_በዓለ_ወልድ

በዓለ ወልድ ወር በገባ በ29 ኛው ቀን የሚከበር ታላቅ በዓል ነው። የወርኃ መጋቢት 29ኛው ቀን በሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል አብሣሪነት በእናታችንና በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ብሥራት ተቀባይነት ከሦስቱ አካል አንዱ አካል ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተፀነሰበት ፍጹም ሰው የሆነበት ዕለት በመሆኑ በዓለ ወልድ ይባላል።

በመሠረታዊ ስያሜውም በዓለ ትስብዕት ወይም በዓለ ፅንሰት ይባላል። ዓመታዊ በዓሉም (ጥንተ ፅንሰት) በመጋቢት 29 ቀን ነው። በዓለ ወልድ በወር ውስጥ ስግደት ከማይሰገድባቸው 3 ቀናት መካከል አንዱ ሲሆን የልዑል እግዚአብሔርን ታላቅ ተአምርና ክብር የምናስብበት ታላቅ በዓል ነው።

እንኳን ለቅዱስ በዓለ ወልድ (በዓለ እግዚአብሔር) ወርኃ  ጥር መታሰቢያ በዓል በሰላም በጤና አደረሰን የበዓለ ወልድ ረድኤት በረከት ይደርብን

ቅዱስ ወልድ ሆይ ስለእኔ ኃጢአት ከሁለት ሺህ ዓመት በፊት በተሰዋውና ዛሬም ትኩስ ሆኖ ኃጢአቴን በሚያጥበው ደምህ ራራልኝ ይቅርም በለኝ ደምህ ዛሬም ስለእኔ ለይቅርታ እንደሚጮህ አምናለሁ አምኜም አቤቱ በደምህ ጥላ ሥር ተጠልዬ ነፍሴን ላንተ አደራ እሰጣለሁ፡፡

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Feb, 19:16


እንዴት አመሻችሁ ተወዳጆቼ እኔ ደኅና ነኝ እንድ መልካም ዜና ይዤ መጥቻለሁ ይኅ የምትመለከቱት በጋራ በመሆን በትርፍ ጊዜያችን ሥራ በመሥራት ገቢያችንን ከፍ የምናደርግበት ፕላትፎርም ነው ፍላጎት ያላችሁ እና በሓሳቡ ምትስማሙ በውስጥ በኩል አውሩኝ እመኑ በከንቱ ነገር ጊዜያችሁን አልገድልም ትወዱታላችሁ ታተርፉበታላችሁ ያያዝያዝኩላችሁ ፎቶ የኔ አካዎንት ነው በጥቂት ቀናት የሠራሁት 1.75 ዶላር ነው ለማውጣትም ቀላል ነው በንግድ ባንክ በቴሌ ብር ማንቀሳቀስ ይቻላል የወር ደመወዝ በ15 ቀናት ውስጥ መሥራት ይቻላል ጎበዝ ከተኮነ ስለዚህ ሳታመነቱ የምታጡትም ነገር ስለሌለ አውሩኝ አብረን እንሥራ በተለይ ሴቶች ፍጠኑ የሚገርም ዕድል ነው ለእናንተ።

@SDS12317212729

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Feb, 15:47


#በዓለ_ቅዱስ_ዐማኑኤል

‹‹#አምስቱን_እንጀራና_ሁለቱን_ዓሣ_የበሉትም_ወንዶች_አምስት_ሺህ_ነበሩ›› ማር፡ 6፥44

በዘመነ ሥጋዌ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ከሞተ በኋላ ወደ በረሃ ሄደ ሕዝቡም ሰምቶ ተከተለው በመሸም ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ሕዝቡን እንዲያሰናብት ጠየቁት ይህም ለዚያ ሁሉ ሕዝብ የሚሆን ምግብ ስለሌለ የሚበሉትን እንዲገዙ ነበር እርሱ ግን ለጊዜው የተገኘውን አምስት የገብስ እንጀራና ሁለት ዓሣ ባርኮ ሁሉንም እስኪጠግቡ ድረስ መገባቸው ተርፎም አሥራ ሁለት መሶብ ተነሣ የተመገበዉም ሕዝብ ሴቶችና ሕፃናት ሳይቆጠሩ አምስት ሺህ ወንዶች ነበሩ፡፡ ‹‹አምስቱን እንጀራና ሁለቱን ዓሣ የበሉትም ወንዶች አምስት ሺህ ነበሩ›› እንዲል ሴቶቹ ያልተቆጠሩበት ምክንያት በዐደባባይ ሲበሉ በሃፍረት ዳር ዳር ስለሚሉ ነው ሕፃናት ደግሞ ከሚበሉት የሚፈረፍሩት ስለሚበዛ ነው፡፡

ጌታችን ያን ሁሉ ሕዝብ በመንደር አጠገብ መመገብ ሲችል ርቆ ወደ ምድረ በዳ የወጣበት ምክንያት ነበረው ይህም

፩ኛ ‹‹ጥንት አባቶቻችሁን ከመንደር አውጥቼ (ከግብፅ አውጥቼ) ዐርባ ዘመን ሙሉ መና የመገብኋቸው እኔ ነኝ አሁንም በሥልጣኔ፣ በተአምራቴ መገብኋችሁ›› ሲላቸው ነው፡፡

፪ኛ ተአምራቱን ከመንደር አጠገብ አድርጐት ቢሆን ኖሮ ‹‹ፈጣን ፈጣን ደቀመዛሙርቱን በጐን ወደ መንደር እየላከ ያስመጣው ነው›› ብለው በተጠራጠሩ ነበር ስለሆነም ለጥርጥር ምክንያት እንዳይኖራቸው አድርጎ ተአምራቱን ገልጦላቸዋል፡፡

ከዚህም ሌላ በበረሃ ያውም በምሽት ሕዝቡን በውኃ አጠገብ በሣር ላይ አስቀምጧቸው መመገቡ ‹‹በፍጻሜው ዘመን በምቹ ሥፍራ በመንግሥተ ሰማያት መንፈሳዊ ምግብ እመግባችኋለሁ በውኃ (በጥምቀት) በሚገኝ ክብርም አከብራችኋለሁ›› ሲላቸው ነው፡፡

በዚህ ታሪክ ውስጥ አምስቱ እንጀራ የአምስቱ አዕማደ ምሥጢር ምሳሌ ነው፡፡ እነዚህም ምሥጢረ ሥላሴ፣ ምሥጢረ ሥጋዌ፣ ምሥጢረ ጥምቀት፣ ምሥጢረ ቁርባን እና ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ናቸው፡፡

ሁለቱ ዓሣ ደግሞ የፍቅረ እግዚአብሔርና የፍቅረ ቢጽ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ፍቅረ እግዚአብሔር ማለት እግዚአብሔር አምላክን በፍጹም ነፍስና በፍጹም ሐሳብ መውደድ ነው፡፡ ፍቅረ ቢጽ ደግሞ ባልንጀራን እንደራስ አድርጐ መውደድ ነው፡፡ ዘዳ፡ 6፥5፣ ማቴ፡ 22፥37 በተጨማሪም እንጀራውና ዓሣው የሥጋውና የደሙ ምሳሌ ነው፡፡

ይህን የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ገቢረ ተአምር በማሰብም ኦርቶዶክሳዋት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓል ሠርታ ዕለቱን በመዘከር ጥር ፳፰ በታቦተ ዐማኑኤል በደመቀ ሥርዓት ታከብራለች፡፡

#ከበዓሉ_በረከት_ያሳትፈን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Feb, 08:27


#እናም_እዘንልን_ማረን_ታረቀን

አቤቱ አንተ የዓለም ንጉሥ ፈጣሪያችን ሆይ ጥፋታችንን ይቅር በለን የሰውን ሁሉ ሥራና ልብ መርምረህ የምታውቀው ሚሥጥር የማይሠወርህ አምላክ ሆይ በኛ ክፋትና በኛ ተንኮል የተወደደችይቱን ሀገራችንን ኢትዮጵያችንን አሥቀጣናት።

መሐሪ የሆንከው አምላክ ሆይ ራስን ከሀገርና ከወንድም አብልጦ ከሚያስወድደው በሽታ ፈውሰን በሠይጣን ኃይል የተበላሸውን ርኩሥ ባህሪያችንን በቸርነትህ አጥበህ ያንተ ማደሪያ ማህደርህ ለመሆን አብቃን

ይህንንም ጸሎታችንን በትሕትና በእመቤታችን በወላዲተ አምላክ አማላጅነት እንለምንሃለን እናም እዘንልን ማረን ታረቀን።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Feb, 06:06


ምን ያህሎቻችሁ እየተዘጋጃችሁ ነው ይኽንን ጉዞ ለመሄድ 🤔 በሉ ቶሎ ቶሎ ተመዝገቡ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

01 Feb, 01:20


#የሃይማኖት_ተክል

#ጥር_24_አባታችን_ተክለ_ሃይማኖት ለሃያ ሁለት ዓመታት የቆሙበት ቀኝ እግራቸው ተሰብሮ መውደቁንና በአንድ እግራቸው ለሰባት ዓመታት ቆመው መጸለያቸውን ቅድስት ቤ .ክ በዓልን ሰርታ በታላቅ ድምቀት ታከብራለች ።

ለሰባ ሁለት ዘመን ያህል በተሠጣቸው ጸጋ መንፈሳዊ አጋንንትን በመስቀል ድል በመንሳት በቃላቸው ተናግረው በእጃቸው ዳሰው ድውይ በመፈወስ ሙት በማንሳት ከዚህም የበዙ ብዙ ተአምራት አድርገዋል ።

#ጻድቁ_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት ለአሕዛብ ወንጌልን ለካሀዲያን አሜንን ለአማንያን ሥርዓተ ምንኩስናን ሲያስተምሩ ቆይተው ሥጋዬን ጠቀምኳት ብለው አንድም በጸጋ ላይ ጸጋ በክብር ላይ ክብር እንዲጨመርላቸው በተወለዱ በዘጠና ሁለት ዓመት እድሜያቸው በደብረ ሊባኖስ ካለችው አሰቦ ገዳመ ዋሻ ውስጥ በመግባት ለሰባት ዓመታት ተጋድሏቸውን ቀጥለዋል ።

ስምንት ጦሮችን አስተክለው ሁለቱን በፊት ሁለቱን በኋላ ፣ ሁለቱን በቀኝ ሁለቱን ደግሞ በግራ በማድረግ እጆቻቸውን በትእምርተ መስቀል በመዘርጋት የክርስቶስን ሕማምና ሞት ነገረ መስቀልን በማሰብ በተመስጦ ሌትና ቀን ያለማቋረጥ በጾምና በጸሎት በአርምሞ ተወስነው ሲጋደሉ ከቁመት ብዛት የተነሣ ጥር አራት ቀን አንዲቱ የእግራቸው አገዳ ተሰብራ የወደቀችበት ቀን ነው ።

ቅዱስ አባታችን በመዓልትና በሌሊት በትጋትና በቁመት በተጋድሎ ብዛት አንዲት የአገዳ እግራቸው ስትሰበር ዕድሜያቸው 92 ዓመት ሆኗቸው ነበር።

በተፈጥሮ ጠባህ ምድራዊ ሰው ስትሆን በሥነ ምግባርህ ሰማያዊ መልአክ ነህና ከልቅሶ ከዋይታው ዐርፍ ዘንድ በወርቅና በእንቁ በተሰራችው በሉዓላዊት ቤትህ ከዚህ ወስደህ አስቀምጠኝ🙏

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

29 Jan, 14:23


፩. አንዳንድ ቀን የሞቱ ሰዎችን የfacebook ገጽ አያለሁ። ከዕድሜያቸው ቀንሰው ዋጋ ሰጥተው የጻፉት ምን ነበር? ያ ያደረጉት ነገር ከሞት በኋላ ላለው ሕይወት አንዳች ቁም ነገር ኖሮት ይሆን? ለሰው ጠቅሞ ይሆን? እግዚአብሔር የሚወደው ነበር ይሆን?

፪. አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የሞቱ ሰዎችን ቃለ መጠይቅ እሰማለሁ። ዋጋ ሰጥተው የተናገሩት ነገር ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር ግንኙነት ነበረው ይሆን? ለምን ነበር በዚህ ምድር የደከሙት? ቃለ መጠይቃቸው ላይ ትኩረት ያደረጉት በምን ጉዳይ ነበር? ያ ጉዳይ በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ አሁን ለሄዱበት ዓለም አዎንታዊ ሚና ነበረው ይሆን?

፫. የሞቱ ሰዎችን መጻሕፍትና የምርምር ውጤቶች (Researches) አነባለሁ። በዚህ ዓለም የደከሙለት ጉዳይ ከዘለዓለማዊው ሕይወት ጋር የተገናኘ ነበር? የትኩረታቸው ዋና ማዕከል ምን ነበር?

፬. ቤተክርስቲያን ስትሔዱ የብዙዎችን መቃብር አስባችሁት ታውቃላችሁ? አንዳንዶቹ ዕቅዳቸውን ሳይቋጩ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶቹ ለምን እንደሚኖሩ ሳያውቁ ያረፉ ናቸው። አንዳንዶች አሁን እኛ ባለንበት ሁኔታ (መጥፎ ወይም መልካም) ሆነው ያረፉ ናቸው።

ሰው ሞትን መዘንጋት የለበትም። ስለዚህ እስካለ ድረስ ለሰው በጎ አስተዋጽኦ አበርክቶ ቢያልፍ መልካም ነው። እግዚአብሔር አድርጉ ያለንን አድርገን ለማለፍ ሕጉን በየዕለቱ እያነበብን እየተገበርን ብንኖር መልካም ነው። ለመሞት አንድ ቀን እንደቀረው ሰው ሆነን እንኑር። ሰውን እንደራሳችን እንውደድ። የእግዚአብሔርን ሕግ እንጠብቅ። ጎበዝ ዕድሜያችንን ለቁም ነገር እናውላት። ሁሉም ኃላፊ ነውና የማያልፈው ላይ ትኩረት እናድርግ። መሞታችን ካልቀረ ደግ ሥራ እየሠራን እንሙት።

#በትረ_ማርያም_አበባው

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

29 Jan, 04:18


#ልጅሽ_ወደ_ሕይወት_ወደ_ክብር_መንግሥት_ይጠራሻል

#የከበረች_እመቤታችን በ49 ዓ.ም ጥር 21 እሑድ ቀን 64 ዓመት ሲሆናት ልጇ ወዳጇ መጥቶ እናቴ ከዚህም ዓለም ድካም የምትለይበት የምታርፊበት ቀን ቀርቧል አላት ያንጊዜ እመቤታችን ደነገጠች።

መደንገጧ ሞትን ፈርታ የዚህ ዓለም ኑሮ አጓጉቷት አይደለም እንዴት የሕይወት እናት ሆኜ እሞታለሁ? የትንሣኤ እናት ሆኜ እንዴት እቀበራለሁ? ሕይወትንንና ትንሣኤን ያዩ ዐይኖቼ እንዴት በሞት ያሸልባሉ ?

ሕይወትንና ትንሣኤን ያቀፉ እጆቼ እንዴት ይገነዛሉ ? አካለ መለኮትን የተሸከመች ጀርባዬ ከመቃብር አፈር ላይ እንዴት ትተኛለች ? ገጸ መለኮትህን የሳሙ ከንፈሮቼ እንዴት በሞት ይዘጋሉ ? በፍጹም አልሞትም ስትለው ነው፡፡

ጌታ ግን አልሞትም ስትለው አልተሟገታትም ያለፈቃዷ ምንም ምን ማድረግ አልፈለገም ምክንያቱም እናቱ ናትና ይወዳታልና ሌላ ማሳመኛ ዘዴ አዘጋጀ ይህውም ልቧን ያውቃል የኀጥአን ነገር እንደማይሆንላት ርኅራኄዋን ስለሚያውቅ መላእክትን ወስዳችሁ በስቃይ ቦታ የሚቃጠሉ ነፍሳትን አሳይዋት ብሎ አዘዛቸው።

እነርሱም ለሰይጣንና በእርሱ ጎዳና ለሚጓዙ ሁሉ ወደ ተዘጋጀ ወደ ጨለማው ዳርቻ አደረሷት ከዚያ ነፍሳት ሲቃጠሉ አየችና አለቀሰች እንዲህም አለች ‹‹ ልጄ ወዳጄ ዛሬ በሲዖል ሲቃጠሉ በራዕይ ያየኋቸውን ነፍሳት እባክህን ማርልኝ አለችው››።

ጌታም ‹‹ እናቴ ! እኔ ዐምስት ሺ ዐምስት መቶ ዘመን በሲዖል ሲቃጠሉ የኖሩትን ነፍሳት ያዳንኳቸው ሞቼላቸው ነው አንቺም እንዲድኑ ከወደደሽ ሙቺላቸው አላት››።

እመቤታችንም ‹‹ አይደለም አንድ ጊዜ ቀርቶ ሰባት ጊዜ ልሙት አለችው ›› ይህንን ቃሏን ምክንያት አድርጎ እርሷም ለነፍሳት ልትሞትላቸው እርሱም ነፍሳትን ሊያድንላት ተስማሙ።

ወዲያው ከደብረ ዘይት ደናግል መጡ የቅርብ አገልጋይዋ ዮሐንስ ከሀገረ ስብከቱ ከኤፌሶን በደመና ተጭኖ መጣ ሐዋርያትም ከየሀገረ ስብከታቸው በመንፈስ ቅዱስ ትእዛዝ በደመና ተጭነው ወደ እመቤታችን ተሰበሰቡ።

ሁሉም በኅብረት ‹‹ የጌታችን እናት ጸጋን የተመላሽ ደስ ይበልሽ ›› እያሉ እየሰገዱ አመሰገኗት ሐዋርያትን እንዲህ አለቻቸው ‹‹ ዕጣን አምጥታችሁ እያጠናችሁ የጌታዬን የኢየሱስ ክርስቶስን ስም ጥሩ ›› አለቻቸው እነርሱም እንዳዘዘቻቸው አደረጉ ።

በዚህ ጊዜ ጌታችንም ከሰማይ ከጌትነቱ ዙፋን አባቷ ዳዊትን የነቢያትንና የመላእክትን ማኅበር አስከትሎ እንደ ግድግዳ ከበውት ወደ እርሷ መጣና አረጋጋት ያዘጋጀላትንም ተድላ ደስታ ነገራት።

የክብር ባለቤት ጌታችንም ‹‹ እንግዲህ ሥጋሽን ተድላ ወዳለበት ገነት አፈልሰዋለሁ ዳግመኛም ሥጋሽን ከነፍስሽ ጋር አዋኅጄ አስነሥቼ መላእክት የሚያመሰግኑበት ተመሳሳይ በሌለው ተድላ ደስታ ባለበት ማደሪያ አኖርሻለሁ›› አላት።

ከሥጋዋም የምትለይበት ጊዜ ሲደርስ ሐዋርያትና ደናግል ትባርካቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኗት እጅዋን በላያቸው ዘርግታ ባረከቻቸው።

በይባቤ መላእክት በመዐዛ ገነት እነሄኖክ እነእዝራ በበገና በመሰንቆ እያመሰገኗት ንጽሕት ነፍሷን ከንጹሕ ሥጋዋ ለይቶ በመለኮታዊ እጆቹ ይዞ በብርሃን ልብስ አጎናጽፎ ወደ ከፍተኛ መኖሪያ ከእርሱ ጋር አሳረጋት ።

ቅዱሳን ሐዋርያት ሥጋዋን እንደሚገባ ገንዘው ወደ ጌቴሴማኒ ተሸክመው እንዲወስዷት አዘዛቸው ሐዋርያትም በአጎበር አድርገው ወደ ጌቴሴማኒ ይዘዋት ሄዱ። ከዚህ በኋላ መልአኩ እመቤታችንን ከዮሐንስ ጋራ በደመና ነጥቆ ወስዶ በገነት ከዕፀ ሕይወት እግር አኑሯታል።

ማርያም ሆይ ስለሁላችን የነፍስ ይቅርታ ከልጅሽ ከወዳጅሽ ከእግዚአብሔር ዘንድ ለምኚልን🙏

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

28 Jan, 05:11


"ሰማይ አድምጥ ምድርም ስሚ"

ይህ ቃል በጸሎተ ሙሴ ላይ የሰፈረ የምስጋና ማንሻ ቃል ነው። የመጻሕፍት ምሥጢር የተገለጠላቸው መተርጉማን ቃሉን ሲፈቱት ለቅዱስ ገብርኤልና በእመቤታችን ይተረጉሙታል። ምድር አድምጥ (ስማ) እንደ ተባለ _ ገብርኤልም ከእግዚአብሔር የተነገረውን ቃል አድምጦ (ሰምቶ) ለእመቤታቸን ሰማያዊውን ብሥራት የነገራት ሲኾን ምድር ስሚ እንደተባለች ደግሞ ከምድር የሆነች እመቤታችንም የገብርኤልን ቃል ሰምታ ጌታን ፀንሳለችና ገብርኤልን በሰማይ እመቤታችንን በምድር መስሎ ያመሰግናቸዋል፡፡

(ዘዳግም 32)

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Jan, 08:13


#ደብረ_ይድራስ_ተራራ_ወስደው_አፅሙን_በተኑት

#ጥር_18 ቀን ቅዱስ ጊዮርጊስ በብዙ ተጋድሎ ውስጥ ሆኖ « እኔ የክርስቲያን ወገን ነኝ እምነቴም በጌታዬ በኢየሱስ ክርስቶስ ነው » በማለት የተመዘዘ ሰይፍ የነደደ እሳትን የከሀዲውን የዲድያኖስ ቁጣ ሳይፈራ መከራን ታግሷል የጌታውን የአምላኩን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት የመሰከረበት ዕለት ሲሆን ።

ቅዱስ ጊዮርጊስም በማይመረምረው ጥበበ እግዚአብሔር በመታመኑ ብዙ መከራ ደረሰበት በጉድጓዳ ብረት ምጣድ ውስጥ አብስለው አቃጥለው አሳርረው ሥጋውንና አጥንቱን ፈጭተው አመድ አድርገው በዕንጨት ቀፎ በማድረግ በዚህ ጥር 18 ቀን ደብረ ይድራስ ወደ ተባለ ረጅም ተራራ ወስደው አፅሙን በተኑት ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ነፍሱን ወደ ሥጋው መልሷት አንድ አካል ሆኖ ወደ ቀድሞ መልኩ ዳግም ተመልሶ አስነሣው ወደ ነገሥታቱም ተመልሶ በመሄድ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ሰበከ ።

ለቁጥር የበዙ አሕዛብ አይተው አደነቁ ከንጉሥ ሠራዊትም ከአሕዛብም ብዙዎችን በጌታችንም አመኑ በማመናቸውም ምክንያት በከሀዲው በንጉሥ ዲድያኖስ ሰማዕትነትን ተቀበሉ ።

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም በታላቅ ድምቀት ይህንን ቀን ታሳቢ በማድረግ በዓልን ሰርታ ታከብረዋለች።

#የሰማዕቱ_በረከት_ይደርብን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

23 Jan, 02:39


#በሃይማኖት_መጽናት

#ጥር_15 ቀን ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት ኢየሉጣን ለክርስቶስ ፍቅር ሲሉ ተጋድሏቸውን እስኪፈጽሙ ድረስ ራሳቸውን ለመከራና ለሞት አሳልፈው በመስጠት ከእግዚአብሔር ቃል ኪዳን ተቀብለው በመንፈቀ ሌሊት አንገታቸውን ተቆርጠው በሰማዕትነት ያረፉበት ቀን ነው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በዓልን ሠርታ በታላቅ ድምቀት ታከብራቸዋለች።

ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት ሰማዕትነት በሚቀበልበት ሰዓት ወርዶ ሕፃኑን ቅዱስ ቂርቆስን የምትሻውን ለምነኝ አለው።

ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ በሰውም ላይ አባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን ብሎ ተማጸነው ።

መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም የለመንከኝን ሁሉ እሰጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ አለው ሕፃን ቂርቆስም በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው ።

ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳረገ ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቂርቆስና በኢየሉጣ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

21 Jan, 15:55


#ጊዜው_ገና_ነው

አንድ ምንጩ የማይታወቅ አስተማሪ የሆነ አፈ-ታሪክ አለ በዚህ አፈ-ታሪክ መሠረት ከዕለታት በአንዱ ቀን አጋንንት ስብሰባ አደረጉ ይባላል ይህንን ስብሰባ የጠራው የአጋንንቱ አለቃም “ዓለምን ሁሉ ከእኔ ጋር ለማሰለፍ እፈልጋለሁ ምን ይደረግ? ማንንስ ልላክ?” ብሎ ጠየቀ ከሥሩ ያሉትም አንድ በአንድ እየተነሱ አሳቦችን ማቅረብ ጀመሩ።

አንዱ ተነሳና “እኔን ብትልከኝ ፈጣሪ የለም ብዬ ሰዎችን ማሳመን እችላለሁ!” ብሎ ተናገረ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱ አይሠራም ብዙዎቹ አያምኑህም ፈጣሪ እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።

ሌላኛው ተነሳና “እኔን ከላክኸኝ ገነትም ሆነ ሲኦል የሚባል ቦታ እንደሌለ አሳምናቸዋለሁ!” አለ። የአጋንንቱ አለቃ ግን “እርሱም አይሠራም ብዙዎቹ ከሞት በኋላ ሕይወት እንዳለ ያውቃሉ” ብሎ መለሰ።

ሌላው ደግሞ ተነሳና “እኔን ላከኝ ፈጣሪም አለ ገነትም አለ ሲኦልም አለ ነገር ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ ለማሰብ ጊዜው አሁን አይደለም ብዬ አሳምናቸዋለሁ” አለ። የአጋንንቱ አለቃም ደስ እያለው “ይህ ጥሩ መንገድ ነው!” በማለት አሳቡን ተቀበለና ላከው ይባላል።

ሰይጣን ማዘግየት ጥሩ ስልት መሆኑን ስለሚያውቅ ለማዘግየት ይፋጠናል በሐዲስ ኪዳን ላይ ቅዱስ ጳውሎስ "ወደ እናንተ ልንመጣ ወደን ነበርና እኔ ጳውሎስም አንድና ሁለት ጊዜ ሰይጣን ግን አዘገየን” 1ተሰ፡ 2፥18 ሲል እናገኘዋለን። ሰይጣን ላያስቀረን ይችላል ግን ቢያንስ ሊያዘገየን ብዙ ይሞክራል።

እርሱ ዓለማዊ ጓዞቻችንን ለአፍታ ስንኳ አውርደን ከእግዚአብሔር ጋር ስላለን ግንኙነት እንድናስብ አይፈልግም ስለ ጸሎት ብታስብ "አሁን ደክሞሃል ጊዜው አይደለም ሌላ ጊዜ ትጸልያለህ" ይልሃል ለመጾም ብትዘጋጅ "አሁን ጉልበት ስለሚያስፈልግህ ብላ የምትጾምበት ጊዜ አይደለም ሌላ ጊዜ ትጾማለህ" ይልሃል ለመስገድ ብትዘጋጅ "ኧረ ተረጋጋ ጊዜው አይደለም ጾም ሲገባ ትሰግዳለህ" ይልሃል ንሥሓ ልትገባ ብትዘጋጅ "ቆይ እንጂ ዘልለህ ጨርሰህ አንዴ ብትታጠበው አይሻልም?" ለማለት የሚቀድመው የለም ቅዱስ ቁርባን ልቀበል ነው ካልክ "አንተኮ ገና ነህ ለወደፊት ጣጣህን ስትጨርስ ቀስ ብለህ አመቻችተህ ትቆርባለህ" ብሎ ያዘናጋሃል።

በዚህ ሁሉ መዘግየት ውስጥ መልአከ ሞት መቼ እንደሚመጣ ማን ያውቃል? ለመንፈሳዊ ነገር ስንነሳ ሰይጣን "ጊዜው ገና ነው" ማለቱ አይቀርም እኛ ደግሞ የእግዚአብሔር ቃል“ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ የመዳን ቀን አሁን ነው” 2ኛ ቆሮ፡ 6፥2 እንደሚል እናስታውስ ለመዳናችን ቀጥሮ አንስጥ።

ፍሬሰንበት ገ/ አድኀኖም
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

20 Jan, 08:24


#ቃና_ዘገሊላ_በአባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ

ወይን የኾነ የቃና ውኀ በመጭመቂያ ጨምቀው በመጥመቂያ ውስጥ የጠመቁት የልማድ ወይን አይደለም ሙሽራ እንዳያፍር ሰርገኞችም እንዲረኩ የተሰጠ የእግዚአብሔር ልጅ የተዐምራቱ ወይን ነው እንጂ፡፡

የጌታ ኢየሱስ እናቱ ወይን እኮ የላቸውም እባክህ ይህን ችግር አስወግድ ብላዋለችና ጌታ ኢየሱስም አንቺ ሴት ከአንቺ ምን አለኝ ገና ጊዜዬ አልደረሰምና አላት በልቡ ለተከማቸ ፍቅሯ በሚሻል ነገር መለሰላት ስለምድራዊ ወይን ለመነችው እርሱም ከጐኑ ስለሚፈሰው የደሙ ወይን በምሥጢር መለሰ፡፡

ጊዜዬ አልደረሰም ያለው የአባቴን ድንቆች በምገልጥበት ከአንቺም በነሣሁት ሥጋ ረኃብንና ጥምን ጭንቁንም ኹሉ በምቀበልበት ከኀጥአን ጋራ በምቀመጥበት አመንዝሮችንም በማነጻበት ሦስት ዓመታት ቀርተውኛልና ከጐኔ በፈሰሰ የምሥጢር ወይን ምእመናንን አረካቸው ዘንድ የምወጋበት ሰዓት አልደረሰም ተብሎ ይተረጐማል፡፡ ይኽን ስለ ተዐምራቱ ወይን ተናግሮታል የሚል ቢኖር እኔም ጊዜው እኮ ደረሰ ማድረጉንም አላዘገየም እለዋለሁ

ያንጊዜም ውኀውን ቀድተው በስድስቱ የደንጊያ ጋኖች እንዲጨምሩ አዘዘ ባሕርዩም ወይን ወደመኾን ተለወጠ ጋኖች ውኀውን ወይን ወደመኾን የለወጡት አይደለም እርሱ ወደጋኖች እንዲቀዱት ያዘዘውን ውኀ ወይን ወደ መኾን ለወጠው እንጂ ጋኖች ውኀውን ወይን የሚለውጡትስ ቢኾን አይሁድ ዘወትር ኹለት ኹለት ሦስት ሦስት ማድጋ በሚይዙ በእነዚያ ጋኖች ውስጥ የሚያጠሩባቸው አይደሉምን፡፡

የቃና ወይን በኦሪት ሕግ ተመሰለች የጠጧትን አላጸደቀቻቸውምና ነገር ግን በመዓዛዋ ጣፋጭነት ልባቸውን ደስ አሰኘች እንዲሁ ኦሪትም ቀድመው የተቀበሏትን አላጸደቀቻቸውም የእግዚአብሔር ቃል ናትና እርሷን በመስማትም ልባቸውን ደስ አሰኘች ስለዚህም ነገር ጳውሎስ በኦሪት ሕግ መጽደቅ በተሳናቸው ጊዜ እግዚአብሔር ልጁን ላከ ከሴትም ተወለደ በኦሪት ያሉትንም ይዋጅ ዘንድ የኦሪትን ሕግ ፈጸመ አለ፡፡

ውኀው በቃና ወይን ወደመኾን እንደተለወጠ እንዲሁ የሙሴ በትር በደብረ ሲና ነቢዩ ከፊቱ እስኪሸሽ ድረስ የሚንቀሳቀስ እባብ ወደ መኾን ተለወጠ ኹለተኛም ነቢዩ ጐንበስ ብሎ እስኪያነሣው ድረስ በትር ወደ መኾን ተመለሰ በዚያም በትር በፈርዖንና በታላላቆቹ ፊት ተዐምራትን አደረገ የጌታ ኢየሱስም የደሙ ወይን በወንጌል ሕግ ተመሰለ ማርካትና ማጽደቅን ችሏል መድኃኒታችን ሥጋዬ እውነተኛ የጽድቅ ምግብ ነው ደሜም እውነተኛ የሕይወት ውኃ ነው ሥጋዬን የበላ የእኔን ሥጋ ስለበላ በሕይወት ይኖራል ደሜንም የጠጣ ሞትን አይቀምሰውም ብሏል እኮን ስለወንጌሉም ያመነ የተጠመቀ ሁሉ ይድናል ያላመነ ግን ይፈረድበታል አለ፡፡

የአምላክን እናት ከልጇ ዘንድ ወይንን ወደ መፈለግ ዜና እንመለስ ወይን እኮ የላቸውም ወይናቸው አልቋልና ብላ ስለምን ለመነችው ከውኀ ወይን እንደሚቀዳ ዐወቀችን ወንጌላዊው ዮሐንስ ይኽም ጌታ ኢየሱስ በቃና ዘገሊላ ያደረገውን ተዐምር የመጀመሪያው ነው ክብሩን አሳያቸው ደቀመዛሙርቱም አመኑበት እንዳለ ከዚያን ጊዜ በፊት እንደዚህ አላደረገምና፡፡

ድንግልስ ውኀውን ወይን ወደ መሆን እንደሚለውጠው አላወቀችም ነገር ግን በአብ ጥላ እንደፀነሰችው በልዑል ኃይልም እንደ ወለደችው ታውቃለችና ስለዚህም ድንግል የምሥራቹን ከነገራት መልአክ ዘንድ አባቱ ሰማያዊ እንደኾነ ተረድታለችና ስለወይን ማለደችው ስለዚህም ነገር በልቧ ድንቆችን የሚያደርግ የእርሱ ልጅ እንደ አባቱ ድንቅ ያደርጋልና ደቀ መዛሙርቱ ስለ ወይን አልማለዱትም ለእናቱም እንደነገራት መልአኩ አልነገራቸውምና የዮሴፍ ልጅ ይመስላቸው ነበር ተዐምራትንም ካደረገ በኋላ ከነቢያት አንዱ እንደኾነ እንጂ የእግዚአብሔር ልጅ እንደኾነ አላመኑበትም.....

#እንኳን_አደረሳችሁ_መልካም_በዓለ_ቃና_ዘገሊላ!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

20 Jan, 05:43


#ቃና_ዘገሊላ

እኛ ስንጨርስ እሱ የሚጀምር አምላክ ስቡሕ ዘተሰብሐ፡፡

በቃና ሰዎች የተዘጋጁበት ኹሉ አለቀ፡፡ የሰው ዝግጅት ሲያልቅ የማያልቀው የእግዚአብሔር ተአምር ጀመረ፡፡

የማያልቀው ወይን እንዲቀዳ ልጇም ተአምሩን ይጀምር ዘንድ ምክንያት የኾነች "የኢየሱስም እናት በዚያ ነበረች፡፡"

ይኽ ታሪክ የአንድ የሰርግ ቤት ታሪክ ብቻ አይደለም ይኽ የዐለም ታሪክ ነው፡፡ ስድስቱ ጋኖች ስድስት ሺ ዘመናትን ይወክላሉ 5500 ዐመተ ፍዳን ማለት ነው፡፡

በስድስት ሺ የዘመን ጋኖች ውስጥ የነበረው ትንቢትና ተስፋ ሲያልቅ 'እኔ የወይን ግንድ ነኝ' ብሎ የነገረን ጣፋጩ ወይን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም መወለዱን… ያስረዳል፡፡

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

19 Jan, 07:34


#ወናሁ_ተርኅወ_ሰማይ_እነሆ_ሰማይ_ተከፈተ ማቴ፡3፥16

#ሰማይ_የተዘጋ_ቤት_አይደለም እንደ ቤተ መቅደስ መጋረጃ የለውም ነገር ግን በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የኀጢአት መጋረጃ የጥንተ አብሶ ተራራ ነበር።

ሰማይም ሳይከፈት ምሥጢራት ሳይገለጡ ዘመናት ተቆጥረዋል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ሲጠመቅ ሰማይ ተከፈተ ድንቅ ምሥጢር ተገለጠ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ከራሱ ላይ ተቀመጠ አብ በደመና አብ የምወደው ልጄ ይህ ነው እረሱን ስሙት አለ ሰማይ ተከፈተ አንድነት ሦስትነት በዮርዳኖስ ተገለጠ የሰማይ መዝጊያው የበደል ደብዳቤ ተቀደደ።

#ሰውና_እግዚአብሔር _አባትና_ልጅ_ሆኑ።

ሰማይ ተከፈተ የመንግሥተ ሰማይ መግቢያ የሆነው የልጅነት ጥምቀታችን በጌታ መጠመቅ ተቀደሰ ኀይል አገኘ።

ሰማያዊ እሳት በዮርዳኖስ ውኀ ላይ በቆመ ጊዜ ውኀው ፈላ እንጅ አሳቱ አልጠፋም።

ለልማዱ በውኋ ላይ አሳት ይጠፋል አይነድም እርሱ ግን የማይጠፋ እሳት ነውና ባሕሩን አፈላው የጥምቀት ውኀ በራሱ ጊዜ ፍል ውኀ ሆነ።

ዛሬ ብዙ ምእመናን ምሥጢሩን ባለማወቅ ልጆቻቸውን ክርስትና ሲያስነሱ ውኀ አሙቀው በፔርሙዝ ተሸክመው ቤተ ክርስቲያን ድረስ ያመጣሉ ቀሳውስቱንም ያስቸግራሉ።

በውኑ ከእናቶቻችን እስቶቭ ከእኅቶቻችን የምድጃ ክሰል ይልቅ የመንፈስ ቅዱስ እሳትነት ውኀውን እንደሚያፈላው ልጃቸው በሙቀተ መንፈስ ቅዱስ እንደሚጠመቅ ዮርዳኖስን መመልከት አልነበረባቸውምን?

የማይጠፋ አሳት ሊያድረበት የተዘጋጀን ሕፃን በሚጠፋ አሳት መለብለብ ከስሕተት በላይነው ሰማይ ሲከፈት መንፈስ ቅዱስ ሲወርድ ልማድ ይቀየራል።

#እንኳን_ለብርሀነ_ጥምቀቱ_አደረሳችሁ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

19 Jan, 05:38


#ይህ_የሐዲስ_ኪዳኑ_ታቦት_ግን...

የኦሪት ጽላት እግዚአብሔር ሙሴንና አሮንን የሚያነጋግርበት በደመና ተከናንቦ ለእስራኤል ብቻ በረድኤት የሚገለጥበት ዙፋን ነበር፡፡

ይህ የሐዲስ ኪዳኑ ታቦት ግን የአምላክ ሥጋና ደም የሚፈተትበት ( ጌታችን ) ሥጋዬን የበላ ደሜን የጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው ሥጋዬን ብሉ ደሜን ጠጡ እያለ ያመኑትን የሚጠራበት የምሕረት
ምሥዋዕ ( መሠዊያ ) ነው፡፡

እናም ለታቦት ክብርና ስግደትም የሚደረግለት ለዚህ ነው በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት መሠረት በታቦታቱ ሁሉ ላይ የተጻፈው ‹‹ አልፋና ኦሜጋ ›› የሚለው የመድኃኔ ዐለም ክርስቶስ ስም ነው።

ከስሙ ጋር ደግሞ በሁሉም ታቦታት ላይ የሚከተለው ጥቅስ በግእዝ ተጽፏል፡፡ ‹‹ ከመ ለስሙ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይስግድ ኲሉ ብርክ ዘበሰማያት ወዘበምድር ›› ‹‹ ይህም በሰማይና በምድር ከምድርም በታች ያሉት ሁሉ በኢየሱስ ስም ይንበረከኩ ዘንድ ›› የሚል ነው ፡፡ ፊልጵ 2፥10

በታቦቱ ፊት የሚሰግድ ሰው ለምን እንደሚሰግድ በታቦቱ ላይ የሚጻፈው ይህ ጥቅስ ያስረዳናል ምክንያቱ ‹‹ ጉልበት ሁሉ ለኢየሱስ ስም ይሰግዱ ዘንድ ›› ስለሚገባ ነው ፡፡

የክርስቶስ ሥጋ እንደሚቆረስ ደሙ እንደሚፈስስ የሚያምን ሰው በዚህ መሠዊያ ፊት በፍርሃት ለክርስቶስ ይሰግዳል ፡፡

ሥጋ ወደሙን ‹‹ ተራ መታሰቢያ ብቻ ነው ›› የሚል ሰው ግን በመሠዊያው ፊት እንዲሰግድና መሠዊያውን እንዲያከብር አንጠብቅም ፡፡

የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በታቦቷ ጽፋ ክብር የምትሠጥ የሐዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያን ልጆች ስለሆንን እግዚአብሔርን እናመሰግናለን ፡፡

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

19 Jan, 04:14


#ከገሊላ_ወደ_ዮርዳኖስ

የሔሮድስ ከተማ ገሊላ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የትውልድም የስብከትም አገሩ ናት።

ከገሊላ ነቢይ አይነሣም ዮሐ. 7፥52 የሚል አባባል በአይሁድ ዘንድ የተለመደ ቢሆንም ኢየሱስ ክርስቶስ አይሁድ በማያውቁት መንገድ በገሊላ መምህር ሆኖ ተነሣ።

ሔሮድስ አስጨንቆ ለሚገዛው ሕዝብ “በጨለማ የሚኖር ሕዝብ ታላቅ ብርሃን አየ በሞት ጥላ አገር ለሚኖሩትም ታላቅ ብርሃን ወጣላቸው” ማቴ. 4፥16 የተባለው ቃል ሊፈጸምላቸው አይገባምን?

የአይሑድ ሊቃውንት በመሠዊያው አጠገብ ስለሚኖሩ የእግዚአብሔር ማዳን ቀድማ እንደምትደረግላቸው ያስቡ ነበር እንጅ እሱስ የማዳን ሥራውን የጀመረው በገሊላ ነበር። የማዳን ሥራውን ለሕዝቡ መስጠት የሚጀምረው ”መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ” ብሎ ማስተማር በጀመረበት ጊዜ ነውና ይህንን የመንግሥተ ሰማያት ምሥጢር ማሰማት የሚጀምርባትን ገሊላ ዛሬ ግን ትቷት ወደ ዮርዳኖስ ምድረ በዳ እየሄደ ነው።

በዚያ ቦታ የቆየ ቃል አለውና ያንን ሊፈጽም ይጓዛል።
በኢያሱ ጊዜ በዮርዳኖስ ውኃ ዳር ድንቅ ነገርን እንደሚያደርግ ተናግሮ ነበር ኢያ. 3፥5
ያንን ድንቅ ነገር ሊያሳየን ዛሬ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሄደ።
ኢያሱ “ሕያው አምላክ በመካከላችሁ እንዳለ....በዚህ ታውቃላችሁ” ብሎ ነበር።

ከልደቱ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ኢየሱስ ክርስቶስ በመካከላችን ሲኖር በጉባኤ፣ በዐዋጅ ነጋሪ ቃል ተለይቶ አልታወቀልንም ነበር፤ ከዛሬ ጀምሮ ግን በመካከላችን የሚኖር እግዚአብሔር እሱ መሆኑን የሚያስረዱ ብዙ ምስክሮች ያሉን ስለሆነ አይተነዋል፤ እናውቀውማለን።

ዐዋጅ ነጋሪው ዮሐንስ “ከእኔ በፊት ነበረ ከእኔም በኋላ ይመጣል” ዮሐ. 1፥30 ብሎ ሲነግረን አብም በደመና ሆኖ “የምወደው ልጄ ይህ ነው” ብሎ የባሕርይ ልጁ መሆኑን ሲያስረዳን፣ መንፈስ ቅዱስም በራሱ ላይ ሆኖ ሲገለጥልን በእርግጥም ሕያው አምላክ በመካከላችን መሆኑን ወደ ዮርዳኖስ ብንወርድ ዛሬ እናውቃለን።

የተስፋይቱን ምድር ሊወርስ የተጠራው ሕዝብ እየመጣ ያለው በዚህ በኩል ነውና ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀበላቸው ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ወጣ።

አባቶቻችንን “በዮርዳኖስ ውስጥ ቁሙ” ብሎ በቀጠረበት ቦታ ለመገኘት ወደ ዮርዳኖስ ሄደ። በደረሰ ጊዜ “ነገ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ድንቅ ነገርን ያደርጋልና ተቀደሱ” ኢያ. 3፥5 ብሎ ኢያሱ የቀጠራቸውን ሕዝቦች ቅዱስ ዮሐንስ “ለንስሐ የሚገባ ፍሬን አድርጉ” ማቴ. 3፥8 እያለ ለቅድስና የሚያበቃውን ትምህርት ሲያስተምራቸው አገኘው።

የኢያሱ ጉባኤ መምህሩ ተቀይሮ ትምህርቱ ተገልጦ አገኘው።
ኢያሱ “ተቀደሱ” ብቻ ብሏል እንጅ ምን ቢያደርጉ እንደሚቀደሱ አልነገራቸውም ነበር የቀረውን ትምህርት ደግሞ ዮሐንስ ገልጦ ንስሐ መሆኑን ነገራቸው።

የመቀደስ ዘመን ስላልደረሰ ሰውን የምትቀድስ የንስሐ ጥምቀትም በሰው ፊት ሳትገለጥ ቆይታ ነበርና ዮሐንስ ዛሬ ገለጣት።
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዮርዳኖስ ሂዶ ከመላእክት ጉባኤ የተጨመረ እንዳይመስላችሁ፤ ቀራጮችና ጭፍሮች ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ ሊጠመቁ ወደ ተሰበሰቡበት ጉባኤ ገባ።
ሕያው ወደ ሙታን ጉባኤ በፈቃዱ ይገባልን? ጻድቁስ በኃጥአን መካከል ቢኖር መልካም ነውን? አወ በከተማ ካሉት ኃጢታቸውን አምነው ከማይናዘዙ ሙታን ይልቅ ኃጢአታቸውን አምነው የሚናዘዙ ኃጥአንን ይወዳልና እነሱ ወዳሉበት መጣ።
የጨረቃ በጨለማ መካከል መውጣት ለሰው ብርሃንን እንደሚሰጥ የክርስቶስም በኃጥአን መካከል መገኘቱ ለኃጥአን ተስፋን ይሰጣል።
ከዮሐንስ በቀር ማንም ሳያውቀው በዚህ ጉባኤ መካከል አደረ።

ቤተ ክርስቲያናችንም ዛሬ ታቦታቱን ከቤተ መቅደስ ይዛ በመውጣት የጌታችንን ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ያደረገውን ጉዞ ታስታውሳለች።
ገዳም ሲሄድ ተከትላው ገዳም የገባች ቤተ ክርስቲያን ወደ መጠመቂያው ስፍራ ሲገባም ተከትላው እንደምትገባ የታመነች መሆኗን ታሳያለች።

ኢያሱ ታቦቱን የተሸከሙ ካህናት በሰፈር ባለፉ ጊዜ ሕዝቡ እንዲከተል እንዳዘዘ ዛሬ ታቦታችንን ተከትለን እንወጣለን። ወደ መጠመቂያው ስፍራ ደርሰን በድንኳን በተቀመጥን ጊዜ ለመጠመቅ ተራውን ሲጠብቅ ያደረውን ክርስቶስን በዐይነ ሕሊናችን እንመለከተዋለን።
ክርስቲያኖች ሆይ! “ኑ ተከተሉኝ” ብሎ አብረነው እንድንጓዝ ሰለፈቀደልን የምናደርገው ጉዞ መሆኑን እያሰብን እንጓዝ።
ከቤተ መቅደስ ተነሥተን ጉዞ ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ ከፊት ከፊታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እያየን ልንጓዝ ይገባናል እንጅ በሳቅና በጨዋታ በዘፈንና በእስክስታ እንዳይሆን መጠንቀቅ ይገባናል።

እንኳን ኢየሱስ ክርስቶስን ተከትለን ይቅርና ኤልያስን የተከተለው ደቀ መዝሙር ዕጥፍ ድርብ ጸጋ የተቀበለው በዚህ አሁን ኢየሱስ ክርስቶስ በሄደበት መንገድ አይደለምን?
የእኛማ እንዴታ!
ጸጋ የምናገኝበት በዓል ያድርግልን፤

#ስምዐኮነ_መልአከ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

18 Jan, 09:29


#እንኳን_ለከተራ_በዓል_አደረሳችሁ!

#የከተራ_በዓል_ምሳሌያት

በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድና የባሕረ ጥምቀቱ መዘጋጀት ሃይማኖታዊ ታሪክና ምሳሌ አለው፡፡ የቃል ኪዳኑን ታቦት አክብሮ መጓዝና ወደ ወንዝ መወረድ የተጀመረው በአሮን ልጅ በአልዓዛር ጊዜ ነው፡፡ ኢያሱ በሙሴ እግር ተተክቶ ሕዝበ እስራኤልን እየመራ ከዮርዳኖስ ወንዝ ሲደርስ ባሕሩ ከሁለት ይከፈልና ወራጁም ይቆም/ይከተር/ ነበር፡፡ እስራኤል ዘሥጋ ወደ ምድረ ርስት ለመግባት የዮርዳኖስን ወንዝ ሲሻገሩ፡- ድንኳን ጥለው የቃል ኪዳኑን ታቦት በድንኳን ውስጥ አድርገው ሌዋውያኑ በዙሪያው፣ ካህናቱ ደግሞ በውስጥ ኾነው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ አድረው በማለዳ ተሻግረዋል /ኢያሱ 3÷8-9/፡፡ ካህናቱ የቃል ኪዳኑን ታቦት አክብረው የወንዙን ዳርቻ በረገጡት ጊዜ እንደ ክረምት ማዕበል ይወርድ የነበረው ውኃ ግራና ቀኝ ተከፍሎ እንደ ግድግዳ ወደ ላይ ቆሟል፡፡

ሕዝቡ ተሻግሮ እስከሚያበቃ ታቦተ ጽዮንን ያከበሩት ካህናት ከወንዙ መሐል ይቆሙ ነበር፡፡ በዚህ መሠረት ‹‹ወተጠምቃ እገሪሆሙ ለካህናት›› ይህም ‹‹የካህናት እግሮቻቸው የዮርዳኖስን ውኃ በመርገጣቸው እንደ ጥምቀት ሆናቸው›› በሐዲስ ኪዳነ ጌታችን ለመሠረተው ሥርዐተ ጥምቀት ምሳሌ ነበር፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን የጥምቀትን ዋዜማ ከተራ ብላ የጠራችው ከዚህ በመነሣት ነው፡፡

ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ የዮርዳኖስ ወንዝ የላይኛው ሸሽቶ ወደ ላይ ተመልሶ ሽቅብ ፈሷል፡፡ የታቹም ወደ ታች ሸሽቷል፡፡ የላይኛው ፈሳሽ ተቋርጦ እንደ ክምር ተቆልሎ ቀርቷል።ቅዱስ ዳዊት የተመለከተውም ይህንኑ ነው። ከአዳም ጀምሮ እስከ ክርስቶስ ድረስ በዘር ይወርድ የነበረው ፍዳ መርገም በክርስቶስ ቤዛነት ተቋርጦ ፤ የታቹም ፈጽሞ መድረቁ ኀጢአተ አዳም የመጥፋቱ ምሳሌ ነው፡፡ እስራኤል ፈለገ ዮርዳኖስን ተሻግረው ወደ ኢያሪኮ መሔዳቸው ምእመናን በጥምቀት ከኀጢአት ቍራኝነት ተላቀው እግራቸውን ወደ ልምላሜ ገነት ወደ ዕረፍተ መንግሥተ ሰማያት አቅንተው ለመሔዳቸው ምሳሌ ነው፡፡ ኢያሱ የጌታ፣ እስራኤል የምእመናን፣ ዮርዳኖስ የጥምቀት፣ ምድረ ርስት የገነት መንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው፡፡

ታቦቱን አክብሮ የሚሔደው ካህን የቅዱስ ዮሐንስ፣ታቦቱ የጌታችን፣ ባሕረ ጥምቀቱ የዮርዳኖስ ወንዝ፣ ታቦታቱን አጅበው የሚሔዱትና በዓሉን የሚያከብሩት ምእመናን ወደ ቅዱስ ዮሐንስ እየመጡ የንስሐ ጥምቀት ሲጠመቁ የነበሩት ሰዎች ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ታቦታቱ በጥምቀት ዋዜማ ከመንበራቸው ወደ ጥምቀተ ባሕር መውረዳቸውና በዚያ ማደራቸው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከማታው ጀምሮ መውረዱንና ተሰልፎ ተራውን ሲጠብቅ ማደሩን ያጠይቃል፡፡ ‹‹ጥምቀት የሞቱና የትንሣኤው ምሳሌ ነው፡፡ ከኃጥአን ጋር ተቆጥሮ እንዲጠመቅና እንዲሰቀል የተጻፈውን ቃል ንስሐና ጥምቀት የማያስፈልገው ሲሆን ነገር ግን ፍጹም ኃጥእ መስሎ በዮሐንስ እጅ ጥምቀትን ለመፈጸም በማየ ዮርዳኖስ ተጠመቀ፡፡››
ጌታችን የተጠመቀበት ወርኀ ጥር በእስራኤላውያን ዘንድ የዝናብ፣ የበረዶ ወራት ነው፡፡ ከወንዝ ዳር ያለ መጠለያ መዋልና ማደር አይቻልም፡፡ በመኾኑም ከዮሐንስ ለመጠመቅ የሚሄዱ ሰዎች ሁሉ በዮርዳኖስ ዙሪያ ድንኳናቸውን ተክለው ያርፉ ነበር፡፡ በዚህ አንጻር ዛሬም በባሕረ ጥምቀት ዙሪያ ድንኳኖች ዳሶች ይጣላሉ፡፡

በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በተለይ በአክሱም የንግሥት ሳባ መዋኛን ‹‹ማይ ሹም›› በጎንደር ዐፄ ፋሲል ያሠሩት ባሕረ ጥምቀት፣ በላስታ ቅዱስ ላሊበላ ያሠራው ባሕረ ጥምቀት፣ በሸዋ የዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ፍርድ መስጫ አደባባይን፣ አርባ አራት ታቦታት የሚያድሩበትን የሸንኮራ ሜዳን “ራቡቴ ወንዝ” በአዲስ አበባ ደግሞ ጃንሆይ ሜዳን /ጃንሜዳን/ ወዘተ ለአብሕርተ ምጥማቃት እንደ ምሳሌ መጥቀስ ይቻላል፡፡ እነዚህ ቦታዎች ዛሬም ድረስ ተከብረው ይገኛሉ፡፡ እኛ በዚህ ወቅት ታቦት ይዘን፣ከወንዝ ወርደን፣ ድንኳን ተክለን በማክበራችን ይፈጸማል፡፡

#ማሕበረ_ቅዱሳን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

18 Jan, 08:00


#የቃል_ኪዳኑ_ታቦት

በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የቃል ኪዳኑን ታቦት ክብር የሚገልጡ ብዙ ገጸ ንባቦች ያሉ ሲሆን በተለየ መልኩ ግን የማይዘነጉ ታሪኮች እና የእግዚአብሔር መገለጫ የሆነውን ታቦት ተአምር የሚያሳዩ ሦስት ክስተቶች አሉ

#በታቦት_አክባሪዎች_እግር_የቆመ_ውኃ

"እንዲህም ኾነ ሕዝቡ ዮርዳኖስን ሊሻገሩ ከየድንኳናቸው በወጡ ጊዜ የቃል ኪዳኑን #ታቦት የተሸከሙ ካህናት በሕዝቡ ፊት ይኼዱ ነበር እንደ መከር ወራት ዅሉ ዮርዳኖስ እጅግ ሞልቶ ነበርና ታቦት ተሸካሚዎቹ ወደ ዮርዳኖስ ሲደርሱ ታቦቱንም የተሸከሙት የካህናቱ እግሮች በውኀው ዳር ሲጠልቁ ከላይ የሚወርደው ውሃ ቆመ። ....... ወደ ዐረባ ባሕር ወደጨው ባሕር የሚወርደው ውኀ ፈጽሞ ተቋረጠ ሕዝቡም በኢያሪኮ ፊት ለፊት ተሻገሩ።" ኢያ፡ 3፥13

#ለታቦት_የሰገደው_ዳጎን(ጣዖት)

"ፍልስጥኤማውያንም የእግዚአብሔርን ታቦት ወስደው ወደ ዳጎን ቤት አገቡት በዳጎንም አጠገብ አኖሩት በነጋውም የአዛጦን ሰዎች ማልደው ሔዱ እንሆም ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግንባሩ ወድቆ ነበር ዳጎንንም አንሥተው ወደ ቀድሞ ስፍራው መለሱት በነጋታውም ማልደው መጡ እንሆ አሁንም ዳጎን በእግዚአብሔር ታቦት ፊት በምድር ላይ በግንባሩ ወድቆ ነበር የዳጎንም ራስ እጆቹም ተቈርጠው በመድረኩ ላይ ወድቀው ነበር የዳጎንም ደረት ብቻውን ቀርቶ ነበር የአዛጦንም ሰዎች እንዲህ እንደ ኾነ ባዩ ጊዜ እጁ በእኛና በአምላካችን በዳጎን ላይ ጠንክራለችና የእስራኤል አምላክ ታቦት ከእኛ ዘንድ አይቀመጥ አሉ።"1ሳሙ፡ 5፥1

#ታቦተ_በመንካቱ_የተቀሰፈዎ_ሰው(ዖዛ)

"ወደ ናኮንም ዐውድማ በደረሱ ጊዜ በሬዎቹ ይፋንኑ ነበርና ዖዛ እጁን ዘርግቶ የእግዚአብሔርን ታቦት ያዘ የእግዚአብሔርም ቍጣ በዖዛ ላይ ነደደ እግዚአብሔርም ስለ ድፍረቱ በዚያው ቀሠፈው በእግዚአብሔርም ታቦት አጠገብ በዚያው ሞተ እግዚአብሔርም ዖዛን ስለ ሰበረው ዳዊት ዐዘነ እስከ ዛሬም ድረስ የዚያ ስፍራ ስም የዖዛ ስብራት ተብሎ ተጠራ።" 2ሳሙ 6:6

እነዚህን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍላተ ንባባት በመረዳት በማመን በመጠንቀቅ በመፍራት በመንቀጥቀጥ በዓላችንን እናክብር አንዳፈር ታቦታትን ለመቅረብ አይደለም በሙሉ ዐይኖቻችን ለማየት አንድፈር በእምነት እንጂ በልማድ የምናከብር አንሁን!

#መልካም_በዓለ_ከተራ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

16 Jan, 17:23


#በእንተ_ጾመ_ገሃድ/ጋድ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ  አሐዱ አምላክ አመ አሡሩ ለጥር በዛቲ ዕለት ሠርዑ አበዊነ መምህራነ ቤተ ክርስቲያን እለ ቀደሙነ ሊቃውንት ዐበይት ከመ ይጹሙ ኵሎሙ መሃይምናን እስከ ምሴት እንዘ ኢይጥዕሙ ምንተኒ መባልዕተ ወበጊዜ ሠርክኒ ኢይጥዐሙ ጥሉላተ ዘእንበለ ዘይትበላዕ በጾም ዐቢይ

ወለእመ ኮነ ዕለተ በይረሙን ዘውእቱ አስተርእዮ በዕለተ እሑድ አው በዕለተ ሰንበተ አይሁድ ይጹሙ በዕለተ ዓርብ እምቅድሜሁ እስከ ምሴት

ወለእመ ኮነ በዓለ ልደት ወበዓለ ጥምቀት በዕለተ ሰኑይ ኢይትከሃል ከመ ይጹሙ በዕለተ ሰንበት ዳዕሙ ይትዐቀቡ እምነ በሊዕ ጥሉላተ (ስንክሳር ጥር 10)

#ትርጉሙንና_ማብራሪያውን_እመለስበታለሁ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

15 Jan, 09:41


የቀደሙት ሰዎች በሰናዖር ከምድር እስከ ሰማይ፣ እስከ አምላክ ማደሪያ የሚደርስ ግንብ ሊሠሩና ስማቸውን ሊያስጠሩ ተነሡ። ነገር ግን በትዕቢታቸው ጠፉ። እነዚህ የባቢሎን ሰዎች ምንኛ ችኩሎች ሆኑ?! ጥቂት ዘመን ቢታገሱ ኖሮ ራሱ አምላክ ከእነርሱ እንደ አንዱ ሰው ሆኖ በግርግም ተኝቶ ያገኙት አልነበር?!

እነዚህ የሰናዖር ሰዎች ትንሽ ቢታገሱ ኖሮ ከምድር ወደ ሰማይ መሻገሪያ የምትሆን በእግዚአብሔር እጅ የታነጸች ታላቋን የብርሃን ድልድይ ድንግል ማርያምን ያገኙዋት ነበር። በዚህችም የብርሃን ድልድይ (መሰላል) እነርሱ ብቻ ሳይሆኑ የሰው ልጆች ሁሉ ስም እንደ ተጠራ አይተው ደስ ይሰኙ ነበር።

====

አቤቱ ጾም፣ ጸሎት፣ መንፈሳዊ ትሩፋቶቻችን የአንተ ረድኤት የሌለባቸው በትዕቢት ያቆምናቸው የሰናዖር ግንቦች አይሁኑብን። እንዲህም ከሆኑ፣ በሥራዬ እያለ ልባችን እንዳይኮራ፣ ዓይናችንም ወደታች እያየ ወዳጆቹን እንዳይንቅ ወደ አንተ የማያደርሱንን እነዚህን የሐሰት ግንቦች አፍርስልን። በእነርሱም ፈንታ በትሕትና እና በፍቅር ያጌጡ ውብ ግንቦችን እናንጽ ዘንድ ረድኤትህን ላክልን።

#ዲያቆን_አቤል_ካሳሁን

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

15 Jan, 06:44


#በሥላሴ እናምናለን #ለሥላሴ እንገዛለን #ለሥላሴ እንሰግዳለን ፤ ከነፋስ ከእሳት ፣ ከውኃና ከመሬት ባሕርያት ፈጥረውናልና የቸርነት ባለቤት የኾነው #የቅድስት_ሥላሴ በረከት እንዲያድርብን የአብ ሰላም ፣ የወልድ ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ ሃይማኖት በመካከላችሁ ይደር ! የሰላም አምላክ ከእኛ ጋር ይኑር ።

ቅድመ ዓለም በነበረ በአንዱ በእግዚአብሔር አብ እናምናለን እናመልካለን አብን በጌትነት በሚመስለው በሚተካከለው በእግዚአብሔር ወልድ እናምናለን እናመልካለን በዓለም ምሉዕ በሆነው በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ እናምናለን እናመልካለን #ቅድስት_ሥላሴ የአምልኮታችን ማዕከል ናቸውና የሚሠዋው መሥዋዕት የሚታጠነው ዕጣን የሚቀርበው ቁርባን ሁሉ የሚያርገው ወደ #ቅድስት_ሥላሴ_ነው ።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

14 Jan, 08:42


#የግዝረት_በዓል_ከጌታችን_ከዘጠኙ_ንዑሳን_በዓላት_አንዱ_ነው

#ጥር_ስድስት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ የፈጸመበት ቀን ነው ቅዱስ ወንጌል « ስምንተኛው ቀን በተፈጸመ ጊዜ ሕጻኑን ሊገርዙት ወሰዱት ገና ሳትፀንሰው መልአኩ ስሙን እንዳወጣለት ኢየሱስ አሉት » ( ሉቃ 2 ፥ 22 )በማለት መዝግቦልናል

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ በሥጋው ግዝረትን እንደ ተቀበለ እንዲህ ሲል ተናግሯል « በእግዚብሔር ፊት የግዝረት ምልክትን አደረገ ፤ ኢያሱም በእስራኤል ልጆች ዘንድ እንዲሁ አደረገ » ብሏል ።

ግዝረት ማለት የወንድ ልጅ የሥጋን ሸለፈት መግረዝ ማለት ሲሆን ሥርዐተ ግዝረት ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠው ለአባታችን ለአብርሃም ነው ይኸውም የእግዚአብሔር ድርሻ የመሆን ምልክት ፣ የእምነትና የቃል ኪዳን ማረጋገጫ ማኅተም ነበር ።

በብሉይ ኪዳን ያልተገረዘ ወደ ተቀደሰው ቦታ አይገባም ፤ የተቀደሰውን መሥዋዕትም አይሳተፍም ከተገረዘው ማኅበረሰብ (ቤተ አብርሃም) ጋር ምንም ዐይነት ዝምድና መፍጠርም ሆነ ጋብቻ መመሥረት አይችልም ከዚህ ወገን መለየት ይኖርበታል ፤ በገንዘብ የተገዛ አገልጋይ ቢሆንም መገረዝ አለበት ።

ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር ።

እነርሱ እንዳሰቡት ሆኖ ቢሆን ኖሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን ባገኙ ነበር ፤ ጌታችን ግን የግዝረትን ሕግ ፈጽሟል ለእኛም በግዝረት ፈንታ ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ እንደበላ በእርሱ ፈንታ ሥጋውንና ደሙን እንደሰጠን ። ( ዘፍጥ 17 ፥ 9 ) ይገልጻል ።

ለአብርሃም በተሰጠው የግዝረት ቃል ኪዳን መሠረት ከአብርሃም የተወለደ ሁሉ ይገረዝ ዘንድ በሙሴ ሕግ ስለተጻፈ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም የአብርሃም ዘር በመሆኗ ጻድቅ አረጋዊ ዮሴፍን « እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንዲሠይመው ብልህ ገራዥ ሰው አምጣልኝ አለችው ።

ዮሴፍም ሄዶ የሚገርዝ ብልህና በሀገሩ የታወቀ ባለሞያ አመጣላት ያ ባለሙያም ሕፃኑን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ አየው እንድገርዘው ሕፃኑን በጥንቃቄ ያዙት አላቸው
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልሶ ባለሙያውን እንዲህ አለው ፦

« ባለሙያ ገራዥ ሆይ ደሜ ሳይፈስ ትገርዘኝ ዘንድ ትችላለህን ? በዕለተ ዐርብ ካልሆነ በቀር ደሜ አይፈስምና » አለው « ያን ጊዜ ጎኔን በጦር ሲወጉኝ ውኃና ደሜ ይፈሳል ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆች ሁሉ መድኃኒት ይሆናል » አለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ቃል ያ ባለሞያ በሰማ ጊዜ ደነገጠ አደነቀም ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሥቶ ከሕፃኑ ጌታ እግር ስር ሰገደ ።

ያን ጊዜም ምላጩ በእጁ ላይ እንደ ሰም ቀልጦ እንደ ውኃ ሆኖ ፈሰሰ የከበረች ድንግል እመቤታችንንም « አንቺ ከሴቶች ተለይተሸ የተባረክሽ ነሽ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ይህ ልጅሽ ስለ እርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው » ብሎ እሷን ወላዲተ አምላክ መሆኗን እሱን አምላክ መሆኑን መስክሯል ።

ሕፃኑም ለዚያ ባለሞያ ዳግመኛ መልሶ እንዲህ አለው « እኔ ነኝ ትገዝረኛለህን ወይስ ተውክ ? ወይም የአባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ እኔ ላድርግ ? » አለው ያም ባለሞያ « የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው » አለው ሕፃኑ ጌታችንም
« የሕዝብ ሁሉ አባቶች የሆኑ አብርሃም ፣ ይስሐቅና ያዕቆብ ናቸው ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጥቷቸዋልና » አለው

ባለሞያውም እኔ ካንተ ጋር እናገር ዘንድ አልችልም በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና አለው በዚያን ጊዜ ሕፃኑ ዐይኖቹን ወደ ስማይ አቅንቶ « አባት ሆይ ለአብርሃም ለይስሐቅ ያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሀቸው ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ » አለ ይህ ብሎ ሲጨርስ ያለ ሰው እጅ በሕፃኑ ሥጋ ላይ ግዝረት ተገለጠች ።

ይኸውም ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማኅፀን እንደ መውጣቱ ፤ የጌታችን ግዝረቱም የማይመረመር ሆነ ወደ ሐዋርያት በተዘጋ አዳራሽ መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር ሁሉ እንዲሁ በረቀቀ ጥበቡ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ በመገረዙ ጌትነቱና ከሃሊነቱ ተገለጠ ።

ያም ገዛሪ ይህን ተአምር አይቶ የሕፃኑንም አነጋገር ሰምቶ እጅግ አደነቀ ፤ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ሦስት ጊዜ ሰገደና « በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ » አለው ከዚህ በኋላ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያደረገውን ተአምራት እየተናገረ ወደ ቦታው ሔደ።

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

14 Jan, 04:49


ኖኅ ማለት ዕረፍት ደስታ ማለት ነው የአዳም 10ኛ ትውልድ በ950 ዓመቱ #ጥር_6 ቀን ዕረፍቱ ነው ብላ ቅድስት ቤተ ክርስቲያ በዓልን ሰርታ ታከብራለች። ዘፍ፡ 9 ፥ 29

አባታችን ኖኅ ከጥፋት ውኃ በኋላ ከመርከብ ወጥቶ መስዋዕት ሠዋ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም « ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሏት » አለው « ጌታዬ የኔ ልጆች ኃጢአት መሥራት አይተውምና ፈርደህ ልታጠፋቸው መብዛቴ ለምኔ ነው ? » አለ፡፡

ጌታም « ምድርን በንፍር ውኃ እንዳላጠፋት ዳመና በዞረ ጊዜ አራት ኅብር አድርጌ ዳግመኛ ቀርጬ አሳይሀለሁ » ብሉ ቃልኪዳን ገባለት፡፡

ቸሩ ጌታችን ሆይ « በእኔና በእናንተ መካከል፥ ሕያው ነፍስ ባለውም ሥጋ ሁሉ መካከል ያለውን ቃል ኪዳኔን አስባለሁ፤ ሥጋ ያለውንም ሁሉ ያጠፋ ዘንድ ዳግመኛ የጥፋት ውኃ አይሆንም። » ብለህ የገባህውን ቃል ኪዳን ዛሬ ለኛ ለልጆችህ ያስፈልገናልና በብዙ የጥፋት ውኃ ውስጥ ነንና አስበን አትርሳን!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

11 Jan, 15:21


ምስክርነት 😎🤗

በቀን 30 ሺ የኢትዮጵያ ብር ገቢ 😍

እኛም ጉዟችን ወደዛው ነው።

ትዝ ይላችዋል Tik tok ሲጀመር ሁሉም አላግጦበት ነበር አሁን ግን ታዋቂ ለመሆን ሰው ከአዕምሮ የወጣ ነገር ያደርጋል።

እና አሁንም እዚህ platform ላይ አላግጣችው ወደ ኃላ ብላችው በርከት ያለ ሰው Join አድርጉ ግርርርርር ሲል መምጣታችው አይቀርም።

ተቀላቀሉኝ አብረን እንደግ

ወ ጥ ር 💪😎🤙


@SDS12317212729 አውሩኝ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

11 Jan, 11:49


የአእላፋት ዝማሬ እንዴት ነበር??

የአእላፋት ዝማሬ በአዲስ አበባ ለ፪ኛ ጊዜ በድሬዳዋ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ መካሔዱ ይታወሳል:: በቅዱስ ፓትርያርኩና በሀገረ ስብከቶች ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ የተጀመረውን ይህንን የአእላፋት ዝማሬ ወደ ፊት በተሻለ መንገድ እንዲቀጥል አደራ የተቀበለው የኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ስለ አእላፋት ዝማሬ ከየአቅጣጫው በጨዋነት የሚሠጡ አስተያየቶችን በአንክሮ ተመልክቶአቸዋል:: የአእላፋት ዝማሬን ለሁለተኛ ጊዜ ማካሔድ የተቻለው "እንዲቀጥል እንፈልጋለን" በሚሉ ድምፆችና ከምእመናን በተሰበሰበ የገንዘብ ድጋፍ መሆኑም ይታወቃል::

ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም የ2018 ዓ.ም. የአእላፋት ዝማሬ ካለፉት ሁለት የአእላፋት ዝማሬዎች በተሻለ ጥራት ለማካሔድ እንዲቻል "የአእላፋት ዝማሬ አበርክቶ ግምገማ" (Impact Assessment) በኢትዮጵያዊው ጃንደረባ ትውልድ ጃን ኢሳይያስ ጥናት ፣ ሥልጠና እና ሥርዓተ ትምህርት ቀረጻ ክፍል የResearch ባለሙያዎች ለማስጠናትና የአእላፋት ዝማሬን መንፈሳዊ ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች የሚተነትን ሰነድ ለማዘጋጀት ከወዲሁ ሥራ ጀምሮአል::

በዚህ ጥናት መነሻነትም ባለፉት ሁለት የአእላፋት ዝማሬዎች ላይ የታዩ በጎ ነገሮች እንዲቀጥሉ መሻሻል ያለባቸውም ነገሮች እንዲሻሻሉ ለጃን አእላፋት ግብአት ሆነው ያገለግላሉ::

ስለዚህ ባለፉት ሁለት የአእላፋት ዝማሬዎች ላይ በአካልም ሆነ በኦንላይን የታደማችሁ እና የአእላፋት ዝማሬ የተሻለ ሆኖ እንዲቀጥል የምትሹ ምእመናንና ጉዳዩ ይመለከተናል የምትሉ ሁሉ ብዙ ስኅተቶቻችንን እንድናርም ጥቂት በጎ ነገሮቻችንን ደግሞ እንድናስቀጥል የሚከተለውን መጠይቅ ጊዜ ሰጥተው በመሙላት እንዲተባበሩን በአክብሮት እንጠይቃለን:: የጥናቱን ውጤትም እንደአመቺነቱ በጃንደረባው ሚድያ ፕላትፎርሞች የምናሳውቅ ይሆናል::

የሃሳብ መወራረስ እንዳይኖርና የእርስዎን የብቻዎን ሃሳብ ለማግኘት እንድንችል ከፎርሙ ውጪ ያለውን የአስተያየት መስጫ ዘግተነዋል:: የሚከተለውን ሊንክ በመጫን በጉግል ፎርም አስተያየትዎን ይሥጡ::

https://forms.gle/cN9NjPqV3SdHiGBe9

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

11 Jan, 06:01


#ከአንተ_ባላውቅም

በገነተ አበው (The Paradise of Fathers) መጽሐፍ ላይ ይህ ታሪክ ተጽፎአል::

አንድ መነኩሴ በበአቱ ቁጭ ብሎ መጽሐፍ ቅዱስን ሲያነብ አንድ ቃል ሊገባው አልቻለም:: ለመረዳት በጣም ሲያስቸግረው "ይኼን ቃልስ እንዲገልጽልኝ ወደ እግዚአብሔር መጸለይ አለብኝ" ብሎ ወሰነ:: ነቢያቱ ያደርጉት እንደነበረውም እግዚአብሔር የቃሉን ፍቺ እስኪገልጽለት ድረስ መጾምና መጸለይ ጀመረ:: ነገር ግን ለሰባ ሳምንታት ያህል እየጾመ ቢጠባበቅም ምንም ነገር ሊገለጽለት አልቻለም:: በየሳምንቱ መጨረሻ ቃሉን ደግሞ ሲያነበውም የበለጠ እየተወሳሰበበት ሔደ እንጂ ጨርሶ ሊገባው አልቻለም::

በመጨረሻም ተስፋ ቆረጠ:: ስለዚህ ሌላ መነኩሴ ጋር ሔዶ ስለዚህ ቃል ትርጉም ሊጠይቀው ወሰነ:: በአቱን ዘግቶ መንገድ ሊጀምር ሲዞር ግን የእግዚአብሔር መልአክ በፊቱ ቆሞ ታየው::

"አይዞህ አትፍራ የፈለግኸውን የቃሉን ትርጉም ልገልጽልህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኬያለሁ" አለው::

መነኩሴው ግራ ገባው
"የጌታ መልአክ ሆይ ሰባ ሳምንት ሙሉ እየጾምሁ እንዲገልጥልኝ ስለምን ቆይቼ ምንም መልስ አላገኘሁም:: አሁን ተስፋ ስቆርጥ እግዚአብሔር ስለምን መለሰልኝ?" አለ በፍርሃት ውስጥ ሆኖ

"እግዚአብሔር ሰባ ሳምንታት ከጾምኸው ጾም ይልቅ ወንድምህን ለመጠየቅ በመሔድ ያሳየኸውን ትሕትና ተቀብሎታል" አለው::

አላዋቂ መስሎ መታየትን ያህል የምንፈራው ነገር የለም:: "አላውቀውም አንተ ንገረኝ" ከማለት ይልቅ ብዙ ሰው ሞት ይመርጣል:: ትንሽ ተምሬያለሁ የሚል ሰውማ ጥያቄ መጠየቅ ዲግሪውን ማቃጠል ይሆንበታል:: የብዙዎቻችን ትሕትና የሚፈቅድልን ሰዓት ለመጠየቅ ብቻ ነው:: "ከአንተ አላውቅም ..." ብለው የሚጀምሩ ዐረፍተ ነገሮች ራሱ ልብ ብለን ከሰማናቸው ይዘታቸው "ከእኔ አታውቅም" ነው::

የእውቀታችንን ውስንነት ለማመን የሚከብደን በሥጋችን ውስጥ ያለችው ለባዊት ነፍሳችን በሥጋዊ እውቀት ራስዋን መገደብ ስለምትቸገርም ነው:: እንደ ቅዱስ ጳውሎስ "አሁን ከእውቀት ከፍዬ አውቃለሁ" ብሎ የእውቀትን ውስንነት ማመን ግን ዕረፍት ይሠጣል:: 1ቆሮ. 13:12

በመንፈሳዊው ዓለም እንዲህ ሲሆን ደግሞ ይበልጥ አሳዛኝ እውነታ ነው::  አላውቀውም አላነበብኩትም አልሰማሁትም ከማለት ይልቅ ሁሉን አዋቂ ሆኖ ለመገኘት ስንል የምንበላቸው ዕፀ በለሶች ብዙ ናቸው::

"ብዙ የማውቀው ነበረ ሰዓት ገደበኝ እንጂ" ብሎ ውስን እውቀቱን ባሕር ለማድረግ የሚደክምና ሰዎች ከተናገረው ከጻፈው በላይ አድርገው እንዲያስቡት የሚገፋፋ ሰው የሚወለደው ካላዋቂነት ፍርሃት ውስጥ ነው::  በጥቂት ንባብ ውስጥ ራስን በጥልቅ ምሁር ዓይን ማየትና "እኔ የማውቀው ማወቄን ነው" ማለት የአላዋቂነት ፍርሃት የሚወልዳቸው ኢሶቅራጥሶች መርሕ ነው::

ከሌላው በታች አላዋቂ መስሎ መታየትን እንፈራለን:: ስለዚህ ሌላውን ከመጠየቅና እንደ ጃንደረባው "የሚመራኝ ሳይኖር እንዴት ይቻለኛል?" "ነቢዩ ይኼን ስለማን ተናግሮታል?" ብሎ ከመማር ይልቅ በራሳችን ለመረዳት ብንሟሟት እንመርጣለን:: ብዙ "የእምነት" denominations የተፈጠሩትም ሌላውን ከመጠየቅ ሞትን በሚመርጡ ትዕቢተኞችና "እንደገባኝና እንደተረዳሁት" በሚል አስተሳሰባቸው እንደነበር ታሪክ ያስረዳናል::

"ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር" ፊልጵ. 2:3

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Jan, 18:10


በካራ ቆሬ ደብረ ገነት ቅዱስ እስጢፋኖስ ጥር 1/2017 ዓ.ም የተሰጠ ትምህርት

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Jan, 15:23


በካራ ቆሬ ደብረ ገነት ቅዱስ እስጢፋኖስ ሰንበት ትምህርት ቤት አባላት የቀረበ ዝማሬ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Jan, 08:29


#የዛሬን_አያድርገውና_ለመስተንግዶም_ሃይማኖትና_ጸጋ_ይጠየቅ_ነበር!

ወኀረዩ እስጢፋኖስሃ ብእሴ ዘምሉእ ሃይማኖተ ወመንፈሰ ቅዱሰ
እምነትና መንፈስ የተሞላ እስጢፋኖስ የሚባል ሰውን መረጡ የሐዋ፡ 6፥5

ይደንቃል ማዕድ ለማዘጋጀትና ለመስተንግዶ እንኳን የሚመረጠው እምነትና ጸጋ ታይቶ ነበር
ያው እምነትና መንፈሳዊ ግንዛቤ ከሌለው ዳቦውንና ፍርፋሪውን ሳይቀር ዘመዴ ወገኔ እያለ ሰው ይለይና በቅዱሱ አገልግሎት ውስጥ የንጹሐን አገልጋዮችን ልብ ያሳዝናልና እነዚያ ለመስተንግዶ የተመረጡትም በጸጋና በእምነት ከፍ ብለው የሚናገሩበትን የጥበብና የጸጋ ኃይል አይሁድ መቋቋም እስኪሳናቸው ድረስ ክርስቶስን ገልጠውታል።

ምሁረ ኦሪት የነበረው እስጢፋኖስ ከብሉይ እስከ ሐዲስ ተርጉሞ አስተማራቸው የሚናገረው ቃል ብቻ ሳይሆን መልኩ ሳይቀር የተለወጦ ወነጸርዎ ኩሎሙ እለ ይነብሩ ዐውደ ወርእዩ ገጾ ከመ ገጸ መልአከ እግዚአብሔር እንዲል የቅዱስ እስጢፋኖስም ፊቱ እንደ እግዚአብሔር መልአክ ሲያበራ በአደባባይ ተመለከቱት
በመልክና በቃል ስብከት ብቻ ሳይሆን በሥራውም አምላኩን ይመስለው ዘንድ በድንጋይ ለሚወግሩት የሚያደርጉትን አያውቁትም ይህንን ኃጢያታቸውን አትቁጠርባቸው ብሎ በታላቅ ድምፅ ጸልዮላቸዋል።

ያ ቅዱስ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ በጎ ንጹሕ ልብ ያለው አገልጋይ ነበርና ብፁዓን ንጹሓነ ልብ እስመ እሙንቱ ይሬእይዎ ለእግዚአብሔር እንዲል በድንጋይ እየተወገረ ሰማይ ተከፍቶለት ሥላሴን በዙፋን ተመለከተ ይህንንም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ይቤ እስጢፋኖስ አንሰ ርኢኩ ወልድ ይነብር በየማኑ ምክር ወሠናይት ማዕከለ ክልኤሆሙ እንዲል የእግዚአብሔርን ክብር ተመልክቷል።

ዛሬ በመከራ ውስጥ ሆነን የምንወገርበት ድንጋይና የወጋሪዎቻችን ጡንቻ ሳይሆን የምንወገርበትን አላማና የምንወገርለትን እግዚአብሔር እንዲታየን ፍርሐት ሳይሆን እምነትና መንፈስ የተሞላ በጎ ኅሊና ያስፈልገናል ተወዳጁ ሐዋርያ ጳውሎስም የአገልጋዮች ሕይወት ይህንን እንዲመስል ለጢሞቴዎስ ሲመክር እንዘ ብከ ሃይማኖት ወሠናይ ግዕዝ እምነትና በጎ ኅሊና ይኑርህ ብሎ ይመክረዋል 1ጢሞ፡ 1፥19

እኛም እንደ ቅዱስ እስጢፋኖስ ምድራዊውን ሳይሆን ሰማያዊውን ነገር ትኩር ብለን እንድናይ አገልግሎትን ታላቅ የሚያደርገው የአገልግሎቱ ደረጃና የማዕረግ መጠን ሳይሆን አገልግሎቱን የምንፈጽምበት ልብ ታላቅነት መሆኑን በቅዱስ እስጢፋኖስ የአገልግሎት ሕይወት መረዳት ይቻላል እጃቸውን ጭነው የሾሙት ሐዋርያት እያሉ ነው እርሱ በዚህ ተጋድሎ ያለፈው በአገልግሎቱ ብርቱና ኃያል መሆኑ እየበዛ እንደሄደ ማደግህ በነገር ሁሉ ይገለጥ የሚለውን የመጽሐፍ ቃል በሕይወታችን እንድንፈጽመው ይርዳን።

#የቀዳሜ_ሰማዕት_ቅዱስ_እስጢፋኖስ_ረድኤት_በረከቱ_ይደርብን።

#በመጋቤ_ሐዲስ_ዘለዓለም_ሐሳቤነህ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Jan, 03:43


#ቅዱስ_እስጢፋኖስ_ቀዳሜ_ሰማዕት

በሐዋርያት ስብከት ቤተ ክርስቲያን ስትስፋፋ በትምህርታቸውና በተአምራታቸው ተስበው ወደ ክርስትና እምነት የተመለሱ ከአይሁድና ከአሕዛብ ወገን የሆኑ ክርስቲያኖች መሬታቸውንና ጥሪታቸውን በመሸጥ ያላቸውን ሀብት አንድነት በማድረግ በኢየሩሳሌም የአንድነት ኑሮን ይኖሩ ነበር፡፡ በሕብረትም የሐዋርያት ትምህርትን በመስማትና በጸሎት ይተጉ እንዲሁም ማዕድን በመባረክ በጋራ ይመገቡ ነበር፡፡ መጽሐፍ ቅዱስም “አንድ ልብና አንዲት ነፍስ አላቸው በማለት የሐዋ፡ 4፥32 ስለአንድነታቸው ፍጹምነት ይነግረናል፡፡

ነገር ግን በቁጥር እየበዙ ሲመጡ በመካከላቸው በማዕድ ምክንያት ልዩነት ተፈጠረ፡፡ ከይሁዲነት ወደ ክርስትና የተመለሱ ክርስቲያኖች በምግብ ክፍፍል ወቅት ከግሪክ የመጡትን ይጸየፏቸው በተለይ ባልቴቶቻቸውን ቸል ይሉባቸው ስለነበር በማኅበሩ መካከል አለመስማማት ተፈጠረ ይህም በሐዋርያት ዘንድ ተሰማ፡፡

ሐዋርያትም “የእግዚአብሔርን ቃል ትተን ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ አይደለም” የሐዋ፡ 6፥2 በማለት ማዕዱንና በውስጥ ያለውን አገልግሎት ያስተናብሩ ዘንድ ሰባት ሰዎች እንዲመረጡ የክርስቲያኑን ኅብረት ጠየቁ፡፡ ምዕመናኑም በአሳቡ ደስ ተሰኝተው መንፈስ ቅዱስና ጥበብ የሞላባቸውን ሰባት ክርስቲያኖችን መረጡ፡፡ ሐዋርያትም እጆቻቸውን ጭነው ረድእ ይሆኗቸው ዘንድ ዲያቆናት አድርገው ሾሟቸው፡፡

ከእነዚህም ዲያቆናት መካከል በቅድስና ሕይወቱ ለክርስቲያኖች ዐብነት የሆነው ሰማዕቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ ይገኝበታል። እስጢፋኖስ የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም “አክሊል” ማለት ነው፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ግእዝ በኋላም ወደ አማርኛ የመለሱት አባቶች በቀጥታ የግሪኩን እስጢፋኖስ የሚለውን ቃል ተጠቅመዋል፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ ምንም እንኳ ስሙ የግሪክ ስም ይሁን እንጂ በትውልዱ አይሁዳዊ ነው፡፡ ወላጆቹ ይህንን ስም ሊሰጡት የቻሉት በፍልስጤም ጠረፋማ ከተሞች ይኖሩ ስለነበር የግርክ ባሕልና ቋንቋ ተጽእኖ አድሮባቸው ይሆናል ተብሎ ይገመታል፡፡

ቅዱስ እስጢፋኖስ በሐዋርያት ጥበቃ የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ከአምላክ ዘንድ ባገኘው የማስተማርና የፈውስ ሀብት ያገለግል ነበር፡፡ በእርሱም ታላላቅ ተአምራት ይፈጸሙ ነበር፡፡ ስለዚህም ሕዝቡ ከፊት ይልቅ እጅግ እየበዛና በትምህርት እየጠነከረ መጣ አይሁድም ይህን ተመልክተው በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ በቅናትና በጠላትነት ተነሡበት ነገር ግን ከመንፈስ ቅዱስ ባገኘው ጥበብና ኃይል እነርሱን በቃልም በድርጊትም ይቃወማቸው ነበርና ሊረቱት አልተቻላቸውም፡፡

ስለዚህም እግዚአብርሔርን፣ ሙሴን ሲሳደብ ሰምተነዋል፤ ሙሴ የሠራልንን ሥርዐት ይለውጣል፤ በዚህ ቤተ መቅደስና በሕጉ ላይ የስድብን ቃል ይናገራል፤ ይህንንም ቤተ መቅደስ የናዝሬቱ ኢየሱስ አፍርሱ ብሏል እያለ ያስተምራል አያሉ ሕዝቡን ሽማግሌዎችንና ጸሐፍትን በማናደድ ይዘው ከሸንጎ ፊት አቆሙት፡፡

ቅዱስ እስጢፋኖስን በሸንጎ ፊት ባቆሙት ጊዜም ፊቱ ልክ እንደ መልአክ ፊት ሆኖ በርቶ ነበር እርሱም ለተከሰሰበት ነጥብ መልስ ሰጠ ከአብርሃም እስከ ክርስቶስ ለእነርሱ የተሰጣቸውን በረከት በመቃወማቸው ከተስፋ ቃል እርቀው እንደተወገዱ ገለጠላቸው ክርስቶስንም ባለመቀበላቸው ወቀሳቸው በዚህም ምክንያት በቁጣ ተነሣስተው ከከተማ ውጭ በመውሰድ በድንጋይ ወግረው ገደሉት፡፡

ቅዱስ እስጢፋኖስ አይሁድ በድንጋይ እየወገሩት ሳለ ሰማያት ተከፍተው ክርስቶስን በአብ ቀኝ ቆሞ ተመለከተ ይህንን ራዕይ የክርስቶስን ትንሣኤን ለማይቀበሉት አይሁድ አሰምቶ ተናገረ እነርሱ ከፊት ይልቅ በእርሱ ጨከኑ በድንጋይም ወገሩት ነገር ግን ቅዱስ እስጢፋኖስ ጌታውን ክርስቶስን መስሎ ነበርና ልክ እንደ መምህሩ ክርስቶስ “አቤቱ ይህን ኀጢአት አትቁጠርባቸው” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኾ  ነፍሱን ሰጠ በቤተክርስቲያንም ታሪክ ስለክርስቶስ መስክሮ ሰማዕትነትን የተቀበለ የመጀመሪያው ዲያቆን ሆኗል፡፡

በደማስቆ መንገድ ላይ ክርስቲያኖችን ያሳድድ የነበረ ሳውል በኋላም ቅዱስ ጳውሎስ ተብሎ ስያሜ የተሰጠው ሐዋርያ  ቅዱስ እስጢፋኖስን በድንጋይ በሚወግሩበት ወቅት በእርሱ ሞት ተስማምቶና ድንጋይን በእስጢፋኖስ ላይ ያነሡትን የአይሁድ ልብስ ይጠብቅ የነበረ ብላቴና ነበር ነገር ግን ቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያ ከሆነ በኋላ የእስጢፋኖስን ቤተሰቦች አጥምቋቸዋል ይህ ደግሞ ድንቅ ነው ቅድስት ቤተክርስቲያናችንም ይህን ቅዱስ የመታሰቢያ ቀን በመስጠት ጥቅምት 17 የዲቁና ማዕረግን በአንብሮተ ዕድ በሐዋርያት የተቀበለበት፤ ጥር 1 ደግሞ ልደቱን በዋናነት ዕረፍቱን ታስባለች፡፡

#በረከቱ_ትደርብን_ጸሎቱ_ትራዳን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

08 Jan, 15:07


#ሰማይ_ዓለም_ሆነ!

የአንጾኪያው ሊቅ ቅዱስ ሳዊሮስ ነገረ ልደቱን ሲያመሠጥር "ሰማይ ዓለም ሆነ ዓለምም ሰማይን ሆነ፡ እግዚአብሔር ሰው ሆኖ በዚህ ዓለም ተገኘ ሰውንም በላይ በአርያም አደረገው፡ በሰማይ የሚቀርበው ምስጋና በዚህ ዓለም ተደረገ፡ በአብ ዕሪና ያለ እርሱ በማርያም ክንድ ተይዞ ታየ፡ እግዚአብሔር አብ በማይመረመር ምሥጢር ያለ እናት የወለደውን ማርያም በማይመረመር ምሥጢር ያለ ዘርዐ ብእሲ ወለደችው። ሃ አበው ዘቅዱስ ሳዊሮስ

ታላቁ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስም በቅዳሴው "መንክርኬ ወመድምም ወዕፁብ ዝንቱ ነገር ምንተኑ እሔሊ ወአነክር ሀልዎተከኑ ምስለ አቡከ በአርምሞ ወበቅድስና ወሚመ ከመ ሕፃን ውስተ ኅፅነ እምከ"ይህ ነገር የሚያስደንቅ እፁብ ድንቅ ነው ማናቸውን አስቤ አደንቃለሁ? በአርምሞና በቅድስና ከአባትህ ጋር መኖርህን ነውን? ወይስ እንደ ሕፃን በእናትህ ክንድ መያዝህን? እያለ ቅዱስ አትናቴዎስ ልደቱን ያደንቃል

እውነትም ይህ ልደት እጅግ ግሩም ድንቅ ነው መናቃችንንና መዋረዳችንን ሊያርቅልን ከሰማያት ወረደ የሚወለዱት ሁሉ የተወለዱበትን አላማ የሚያውቁትና የሚረዱት ከተወለዱ በኋላ ነው እርሱ ግን አላማ ይዞ ተወለደ፡ ለእኛ ለሁላችንም መንፈሳዊ ልደትን የሚያድል አላማን ይዞ ተወለደልን።
ቃል ሥጋን ነሣና ገና ከልደቱ ጀምሮ ተዋሕዶን አንድነትን አጸናልን ከቤተ ሕዝብና ከቤተ አሕዛብ ተወልዶ ወደ አንድነት አመጣን፣ ከከበሩት ከሰብአ ሰገል ከነገሥታቱ ከተናቁት ከእንስሳት ከአህዮቹ ሳይቀር እስትንፋስን ተቀበለና የሚናቅ ፍጥረት አለመሆናችንን መሥዋዕት ከሚሆኑና ከማይሆኑ እንስሳት ሳይቀር መባቸውን ተቀብሎ ለቤተ አሕዛብም መምጣቱን አስረዳ።
በመላእክት ማኅበር ቦታ ሊሰጠን በከብቶች በረት ተወለደ
የጸጋ ልብስ ሊያጎናጽፈንና በክብር ሊጠቀልለን በጨርቅ ተጠቀለለ።

ታላላቅ ነገሥታት በእናቱ እቅፍ ላይ ላለ ሕፃን ሰገዱለት እጅ መንሻም አገቡለት እረኞችና መላእክት በአንድነት አመሰገኑ ይህ የአምላክ መወለድ ለእኛ መንፈሳዊ ልደትን የሚያሰጥት በደላችንን የሚደመስስ ሕዝብና አሕዛብን፣ ሰውና መላእክትን፣ ሰውና እግዚአብሔርን አንድ ያደረገ አዲስ ልደት ነውና ወደ ዓለም ተወልዶ ወደ ሰማይ እንድንወለድ ላደረገን አምላክ ክብርና ምስጋና ይሁን።

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

07 Jan, 14:43


የአእላፋት ዝማሬ ለፓሪስ ኦሎምፒክ ጸያፍ ትርዒት ምላሽ ሠጠ
| ጃንደረባው ሚድያ | ታኅሣሥ 2017 |
አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

የ2017 ዓ.ም. የአእላፋት ዝማሬ ላይ "የገና መልእክት ከኢትዮጵያውያ ሰዎች ወደ ኦሎምፒከኞች" (A Christmas Message from Myriads to Olympiads) በሚል ርእስ የሁለት ደቂቃ አኒሜሽን ታየ:: የዚህ መልእክትም ዋነኛ ሃሳብ ከአራት ወራት በፊት በፓሪስ ኦሎምፒክ መክፈቻ ላይ የጸሎተ ሐሙስ ሥዕል ላይ ጸያፍ መልእክቶችን በማስተላለፍ የተደረገውን ተሳልቆ ለጸሎተ ሐሙስ ሥዕልና ለከበረው የክርስቶስ ደም ክብር የምትሠጠው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ምን ያህል እንዳስቆጣ ለማሳየት ነው:: "እነርሱ በስሙ ሲዘብቱ ኢትዮጵያ ግን ዳግመኛ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች" (When they mock his name in vain, Ethiopia lifts her hands to God again) የሚል መልእክት ያለው ይህ ቪድዮ የፓሪስ ኦሎምፒክ አዘጋጆችን ድርጊት በክርስቶስ ላይ የጥላቻ ጦር ከሰበቀው ከንጉሥ ሔሮድስ ድርጊት ጋር በማመሳሰል የተሠራ መሆኑን የአኒሜሽኑ ዳይሬክተር ወ/ሪት ቅድስት ፍስሓ ገልጻለች::

"ዓለም አቀፍ መክፈቻ ሥነ ሥርዓቶችና ምርቃቶች በተካሔዱ ቁጥር በክርስትና መቀለድና ሰይጣናዊ ትርዒቶችን ማሳየት እየተለመደ መጥቶአል" ያሉት የአኒሜሽኑ ክሪኤቲቭ ዳይሬክተር ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ በበኩላቸው "ዓለም አቀፍ ሚድያዎች ከፍተኛ ሽፋን እየሠጡት ባለው በአእላፋት ዝማሬ ላይ ለዓለም አቀፉ ተመልካች የሚሆን መልእክት ለማስተላለፍ አጋጣሚውን ተጠቅመንበታል" ብለዋል::

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Jan, 08:31


መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ፤
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤
ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያት በሙሉ፤

በምሉእ ፍቅሩ ሰውን ከባርነት ወደ ነጻነት ለመመለስ በሥጋ ሰብእ የተወለደው ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የልደት በዓል በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ፡፡

“ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ለዘሠምሮ ለሰብእ፤ ክብር በሰማያት ለእግዚአብሔር ይሁን›› በምድርም እጅግ ለወደደው የሰው ልጅ ሰላም ይሁን” (ሉቃ ፪÷፲፬)
ይህ ቃለ ሰላም በጌታችን ዕለተ ልደት የተነገረ ነው፣ ቃሉ የተነገረው እንዲሁ እንደ ተራ ነገር ሳይሆን በቃለ መዝሙር እየተደጋገመ ነው፡፡ የተዘመረውም በምድራውያን ደራሲዎች ሳይሆን በሰማያውያን መላእክተ እግዚአብሔር ነው፣ የያዘው መልእክትም ሰማያውያንና ምድራውያንን ሁሉ ያካለለ ነው፡፡ የመልእክቱ ገዢ ሓሳብም አምላክ ከሰውነታችን ጋር ባለመለያየት፣ ባለመጠፋፋት፣ ባለመቀላቀል፣ ባለመዋዋጥ፣ ባለመለዋወጥና ያለባዕድና አንድ አካል፣ አንድ ክዋኔ፣ አንድ ጠባይ ሆኖ በተዋሕዶ ተገልጾኣልና እግዚአብሔር ይክብር ይመስገን፡፡ የተዋሕዶውም ምስጢር ሰላምን ያሰፍናልና እግዚአብሔር ሰውን በእጅጉ መውደዱ ከዚህ ተዋሕዶ ዓውቀናል የሚል ነው፡፡

በእርግጥም እግዚአብሔር ሰውን ለመውደዱ ከዚህ የበለጠ ማሳያ ወይም ማስረጃ የለም፤ እንከን የለሽ ንጹህ አምላክ የእኛን ኃጢአተኛ ሰውነት አካሉ አድርጎ ተወለደ ሲባል ላስተዋለው ሰው ምንኛ ቢወደን ነው የሚለው ጥልቅ አድናቆትን ያጭራልና ነው፡፡ይህ ብቻም አይደለም በዚህ ነገረ ተዋሕዶ ምክንያት ሰውነታችን አምላክ ሆኖ በመንበረ ጸባኦት እንዲቀመጥ መብቃቱ የድኅነታችንና የክብራችን ከፍታ ምን ያህል አስተማማኝ ደረጃ ላይ እንደደረሰ መንፈሳችን በአንክሮ ይረዳዋል፡፡ድምር ውጤቱም በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ፍጹምና አስተማማኝ ሰላም መፈጠሩን ያስረዳናል፤ ሰማያውያኑ መላእክተ እግዚአብሔር በመዝሙራቸው ያበሰሩን ይህንን የምስራች ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

እኛ ክርስቲያኖች እግዚአብሔር ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር በእጅጉ ይወደናል ስንል እንዲሁ ከሜዳ ተነሥተን ኣይደለም፡፡ በበደላችንና በኃጢአታችን ሳይጸየፈን ሰውነታችንን በረድኤት ወይም በኅድረት ያይደለ በኩነት ተዋሕዶ ወደ አምላክነት ደረጃ ከፍ ስላደረገው ነው እንጂ፡፡ እግዚአብሔር በዚህ ፍጹምና ምሉእ ፍቅሩ ሰውነታችንን በመበረ ጸባኦት ኣስቀምጦ መላእክት ሳይቀሩ ፍጥረታትን በሙሉ እንድንገዛ አድርጎናል፤ ምክንያቱም መላእክት በዕለተ ልደት የዘመሩለት በተዋሕዶ አምላክም ሰውም ለሆነ ለቤተ ልሔሙ ሕፃን እንጂ ለመለኮት ብቻ ኣይደለምና ነው፡፡ የዕለተ ልደት መዝሙር ዛሬም በሰማያትም ሆነ በምድር በተዋሕዶ ሰውም ኣምላክም የሆነ አንዱ ኢየሱስ ክርስቶስ ይመለክበታል፣ ይመሰገንበታል፡፡የሰማዩና የምድሩ ዕርቅ ወደ ኋላ ላይመለስ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ በዚህ ተከናውኖኣል፣ የእግዚአብሔር ፈቃድ የሰውም አዋጭ ምርጫ ይህ ዕርቅ ተጠብቆ እንዲኖር ነው፣ ያለ ዕርቅ ሰላም ሕይወት የለውምና፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

የእግዚአብሔር ክብርና ሰላም በእጅጉ የተሳሰሩና የተቆራኙ ናቸው፤ እኛ እግዚአብሔርን ካከበርነው፣ ካዳመጥነው፣ ከታዘዝነውና ከተከተልነው ሰላም አለ ማለት ነው፡፡ ለሱ ካልታዘዝንና እሱን ካላከበርን ግን ዘላቂ ሰላምን ማግኘት ፈጽሞ የማይታሰብ ነው፤ ምክንያቱም ሰላምን ጨምሮ መልካም ነገር ሁሉ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ነውና፡፡ ዛሬ በሁሉም የዓለማችን ማዕዘን የሚታየው የሰላም መደፍረስ እግዚአብሔርን ካለማክበራችንና ለሱ ካለመታዘዛችን የተነሣ እንደሆነ መዘንጋት የለብንም፡፡ ዓለም ከእግዚአብሔር ቃል ርቃ ለመሄድ በእጅጉ እየኳተነች ነው፤ በዚህ እኩይ ተግባርዋ ደግሞ እግዚአብሔር ለስጋትና ለጉስቁልና አሳልፎ እየሰጣት ነው፡፡ እግዚአብሔር በምስጢረ ሥጋዌው ቢታረቃትም ዕርቁን ማክበር አቅቶአታል፤ ይህንን የእግዚአብሔር ጸጋ ቸል ብላ የምታደርገው ሩጫ የትም ሊያደርሳት እንደማይችል ብታውቅና በንስሓ ብትመለስ እግጅ ተጠቃሚ ትሆናለች፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!

የእግዚአብሔር ቃል “እናንተስ ከማይጠፋ ዘር ተወለዳችሁ” ብሎ ተስፋውን እንደነገረን ምድባችን ከማይጠፋ ዘር እንዲሆን ክርስቲያኖች የሆን ሁላችን በአእምሮ ጐልብተን፣ በሥነ-ምግባር ኣምረን፣ ጤናማ ሕይወትን ልንመራ ይገባናል፡፡

የአምላካችንን በዓለ ልደት ስናከብር ነገረ እግዚአብሔርን፣ ነገረ ፍቅርን፣ ነገረ ዕርቅንና ነገረ ሰላምን በማኅበረሰባችን የማሥረጽ አጀንዳ ይዘን ልናከብር ይገባል፡፡
ጠቡ ፣ ጥላቻው፣ መለያየቱ፣ መጠፋፋቱ፣ ለወንድሜ ከማለት ይልቅ ለኔ ለኔ ማለቱ ሲጎዳን እንጂ ሲጠቅመን ኣላየንም፡፡ አሁንም ወደ ልባችን እንመለስና በፍቅር፣ በዕርቅና በእኩልነት፣ በስምምነትና በወንድምነት ወደሚገኝ አንድነት እንምጣ፤ የልደቱ መዝሙር ያስተማረን ይህና ይህ ብቻ ነውና፡፡ በሌሎቹ ክፍለ ዓለማት እንደሆነው ሁሉ በሀገራችን የተከሠተው አላስፈላጊ ግጭት ብዙዎችን አሳጥቶናል፤ ብዙዎችንም ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሎ ሜዳ ላይ ፈሰው የሰቆቃ ኑሮ እንዲገፉ አድርጎብናል፡፡ የሀገር ሀብት እንዲወድም ሆኖአል፤ ልጆቻችን ምናለ ከእንግዲህ ወዲህ ቢበቃንና ምድሪቱን የሰላም አየር እንድትተነፍስ ብንፈቅድላት፤ ይህ የወቅቱ የቤተክርስቲያናችን ዋነኛ መልእክትና ጥሪ ነው፡፡

በመጨረሻም፡-

በዓለ ልደት የእግዚአብሔር በዓል ነውና፣ እግዚአብሔር በምድራችን ሰላምን ያወርድ ዘንድ ካለን ከፍለን ለተፈናቃዮች፣ ለነዳያን እና ለአካል ጉዳተኞች በመለገስ በዓሉን በመንፈሳዊ ደስታና በሰላም እንድናከብር አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤

መልካም በዓለ ልደት ያድርግልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ
ተክለሃይማኖት
ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Jan, 06:23


#መልካም_እረኛ

ወይእዜኒ ግብኡ ኀበ ኖላዊክሙ ወዐቃቢሃ ለነፍስክሙ
አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል 1ጴጥ 2:25

ከታኅሣሥ 21 እስከ 27 ያለው አንድ ሱባዔ ኖላዊ ይባላል
የሚሰበስበውና የሚያሰማራው፣ የሚጠብቀው፣ ከጠላት የሚታደገው እውነተኛ እረኛ አጥቶ ለተበተነ ፍጥረት ሁሉ እረኛ ሆኖ ይሰበስብ ዘንድ የእረኞች አለቃ ወደ ዓለም መጣ
ኢሳ 53 ሕዝ 34 ላይ መልካም እረኛ የሌላቸውን የበጎችን መከራ ምን ያህል አስጨናቂ እንደሆነ ተገልጧል

ክርስቶስ ግን እውነተኛ እረኛ መሆኑን ሲያጠይቅ በእንስሳት በረት ተወለደ
ለትጉሃን እረኞች ልደቱን ገለጠ
በመጨረሻም አነ ውእቱ ኖላዊ ኄር ዘበአማን ወኖላዊሰ ኄር ይሜጡ ነፍሶ ቤዛ አባግዒሁ እውነተኛ እረኛ እኔ ነኝ እውነተኛ እረኛ ስለበጎቹ ነፍሱን ይሰጣል ብሎ በሞቱ ሕይወቱን በርሱ ሞት ሕይወቱን ሰጠን

በጎቹ እርሱን መከተል ድምፁን መስማት ይጠበቅባቸዋል፡ዛሬ ግን የረኛቸውን ድምፅ የሚሰሙ በጎች እየመነመኑ ብዙዎች እረኛቸው ላይ ሳይሆን ምንደኞችን መስማትና መከተል የዘወትር ተግባራቸው ነው

ይህ እረኛ ከእረኞች ሁሉ ይለያል በጎቹን በብቱ አቅፎ በጫንቃው ተሸክሞ ነው የሚጠብቃቸው ኢሳ 40:11
እረኛ በጉን አርዶ፡ይበላዋል ወይ ይሸጠዋል የእኛ እረኛ ግን በጎቹ በተራቡበት ጊዜ ራሱን ምግብ፡አድርጎ አቀረበላቸው
በተጠሙ ጊዜ ራሱን ጠጡት ይህ እረኛ የዘለዓለም ምግብና መጠጣችን ነው ለበጎቹ የታረደ እውነተኛ በግ እርሱ፡ብቻ ነው ይሄንን የእረኝነት ሥራ፡ካሳየ በኋላም የእረኞች አለቃ ነውና የእረኝነት አርአያን አስተምህሮ አሳያቸውና

በመጨረሻም ወደ ሰማይ ከማረጉ በፊት ለሐዋርያት የሰጠው የመጨረሻ ትዕዛዝ በጎቼን ጠብቁ ነው
ዮሐ 21 ዛሬ፡ዛሬ ግን በጎችም ለመጠበቅ አይመቹም እረኞቹም እራሳቸውን አሰማርተው በጎቹን የሚጠብቅ ጠፍቷል ግዴለሹ በዝቷል

እውነተኛ እረኞች በምንደኞች እየተፈተኑ መንጋው ለምንደኞች ተሰጥቶ በውኃ ጥምና በርሃብ የሚቀጣ ሆኗል
እንደ ሕጉ ረኞች በጎችን መጠበቅ ነበረባቸው አሁን አሁን ግን በጎች እረኞችን በመጠበቅ ላይ ናቸው፡
እረኞች በጎቹ እንዳይጣሉ መጠበቅ ነበር ሥራቸው አሁን ግን እረኞች ካህናት እረኞች አለቆች እረኞች መምህራን እርስ በርስ አልስማ ብለው በጎች ምዕመናን እረኞችን ለማስማማትና ለማስታረቅ ፍዳቸውን ያያሉ
እውነት ለመናገር አሁን አሁን እረኞች በጎችን ሳይሆን በጎች እረኞችን የተሸከሙበት፡ዘመን ላይ ደርሰናል
አሁን የመቅደሱም ሆነ የሀገሪቱ መሠረታዊ ችግር እረኞች አልስማማ ብለው በጎች ለእረኞች የሚያዝኑበት ወቅት ላይ ናቸው የበጎቹ ምኞት እኛን መጠበቁ ይቅርና፡ምነው በተስማማችሁ የሚል ነው

በሀገራዊ ኃላፊነትም ይሁን፡በመንፈሳዊ አገልግሎት የተሰጠንን የእረኝነት ሥራ በአግባቡ ፈጽመን ብንገኝ ከበጎቹ በላይ ተጠቃሚዎቹም እኛው እንደመሆናችን ደህና እረኝነቱን በተግባር አሳይቶ ያለፈው ታላቁ እረኛ ቅዱስ ጴጥሮስም በአገልግሎት ለሚመስሉት እረኞቹ ሲመክር " የእረኞቹም አለቃ፡በሚገለጥበት ጊዜ የማያልፈውን የክብር አክሊል ትቀበላላችሁ። ብሎ መክሯል 1ጴጥ 5:4

የእረኞች አለቃ የበጎቹ ጌታ ሆይ የመልካም እረኝነቱን ዘመን መልስልን
እኛም የባዘን በጎችህ ወደ እቅፍህ የምንቀርብበትን የንስሐ ጎዳና ምራን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

04 Jan, 10:49


#ዘቀዳሚት
◈◈ የምናየው ◈◈

የተጋጩ ሰዎችን ሸምግሎ ማስታረቅ ትልቅ ትዕግስትና ጥበብ የሚጠይቅ ነገር እንደኾነ ጉዳዩ የደረሰበት ሰው ምስክር ነው። ኹለቱንም አካላት ላለማስከፋት ፤ በዳይና ተበዳይ ብሎ ጎራ ሳይለዩና ሳይወግኑ መሐል ኾኖ መዳኘት ፤ የተከፈለው ተከፍሎ ዕርቅ ለማውረድ መስዋዕትነት ይጠይቃል።

አንድ ወንድም የተጣሉበትን ኹለት ወዳጆቹን ሊያስታርቅ ምሳሌ ሲሰጥ "የምናየው እውነት ነው ፤ ያላየነው ደግሞ ግምት ነው" ሲል አደመጥኩት። "በዐይኔ በብረቱ ተመለከትኩ" ሲል የነበረው ተበዳይ ፤ ካየው ነገር በኋላ ስለተፈጠረው ነገር የገመተው ልክ እንዳልኾነ ፤ በሰዎች አሉባልታም ምክንያት መሐላቸው ሰይጣን እንዳይገባ በማሰብ ፤ የተጠቀመው ምክር ስለነበር ጥበቡ ደነቀኝ። ንግግሩን የሚያፋርሱ ኹኔታዎች ቢኖሩም ግን ቁም ነገር የሚፈለቀቅበት ውብ ገለጻ ነው።

የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጅ ነህ? ግን ከክርስትና ቀን ጀምሮ ደጇን ረግጠህ ዐታውቅም? በዓለም ሀሳብ ስትዳክር ጊዜ አልበቃ ብሎህ ቅዱስ ወንጌልን አልተማርክም? ኃጢአተኛ ነኝ እኔማ ፊቱ አልቆምም ብለህ እንደዋዛ ዘመናት ተቆጠሩ? በዓለም የመኖር ትርጕሙ ምን እንደኾነ ሳይገባህ ከቤተ ክርስቲያን ርቀህ ከርመሃል? ወይስ መመላለስህ የእግር ብቻ ኾነ? እግርህ እንጂ ልብህ እግዚአብሔር ደጅ ተጠግቶ አያውቅም?

ወይስ "ኢየሱስን አያውቁትም" የሚሉትን አሉባልታ ሰማህ? ወንጌል አይሰብኩም የሚል ወሬ ውስጥህን አሸብሮታል? ቅዱሳንን ያመልካሉ ፤ ጣዖቶቻቸው ብዙ ናቸውስ ብለውሃል? የተከፈለልህ መኾንህንና ካንተ ማመን በስተቀር ምንም እንደማይጠበቅብህስ ነግረውሃል? ታዲያ ምን ዐሰብኽ? ልብህ ወላወለ?

በቅጡ ያላየኸውንና ያልተረዳኸውን እውነት ለመረዳት ጥረት ማድረግ ትተህ ያላየኸውንና ያላወቅኸውን ለማመን ለምን ትቸኩላለህ? በሞት ለመወሰድ መቸኮልማ የተስፋ መቁረጥ ምልክት ነው! አንተ ግን ክርስቲያን ነህ! ተስፈኛ ነህ! በምድር ብቻ ሳይኾን በሰማይም ያማረ ቤት ያለህ ተስፈኛ ነህ! ውስጥህ ሲሸበር ፤ ልብህ ሲወላውል አንድ መፍትሔ አለ 'ማየት!'። የምታየው እውነት ነው ፤ ያንን እውነት ተከትለህ ብዙ ባወቅህና በኑሮ በተለወጥኽ ቁጥር ክርስቲያን ትኾናለህ። የስም ሳይኾን የግብር ክርስቲያን! ስለዚህ ማየት ትሻለህ?

በቃ ለአንድ ቀን ቤተ ክርስቲያን ና! እዚህች ቅድስት ስፍራ ብትመጣ ማየት የፈለግኸውን ታየዋለህ። አልተሰበከም የተባለውን ንጉሥ በክብር ዙፋኑ ላይ ኾኖ ፤ ከሠራዊቱ ጋር ሲመሠገንና የአምልኮ ስግደት ሲሰገድለት ትመለከታለህ። አልተነገረም የተባለለትን አምላክ ሕይወት የኾነ ሥጋውና ደሙ ሲፈተት ብዙዎችም ለመዳን ሲበሉትና ሲጠጡት ዐይንህ ያያል።

ሳያዩ በማመን የሚገኘው ብጽዕና ለዘመኔ ከብዷልና "ማየት ማመን ነው" የሚል የሀገሬውን ብሂል ይዘህ አንዴ ብቻ ና! የልቡናህን ዐይን ከፍተህ ከመጣህ ውበቱ ይገዛሃል። በጸሎቱ ፤ በምስጋናው ፤ በዝማሬው ፤ በስብከቱ ፤ በምሕላው ፤ በአለባበስ ፤ በአነጋገሩ ኹሉ በቀራንዮ ላንተ ሲል የተሰቀለልህን ጌታ በዙፋኑ ላይ ኾኖ ታገኘዋለህ። ብቻ አንዴ ና!

ከመጣህና ካየህ ግን አንድ ነገር እርግጠኛ ነኝ ፤ ማዳኑን ዐይተህ ከአረጋዊው ስምዖን ጋር “ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋል” ብለህ ትዘምራለህ።(ሉቃ 2፥30) አልያም እንደቅዱሳን አባቶችህ የሐዋርያቱን ዐይን ዐይንህ አድርገህ "ዐየነው ዳሰስነው ከእርሱም ጋር በላን ጠጣን አኹንም ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው የማይሞት ፤ ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደ አቤቱ ይቅር በለን እያልን እናመሥግነው" ማለትን ገንዘብ ታደርጋለህ።

ይህ ኹሉ ስለእርሱ መሐሪነት የሚኾን ነውና ተመሥገን እንለዋለን! የተጎበኘ ሰው "ተመሥገን" ብቻ ነው መልሱ ፤ ለእርሱ ምን ልናደርግለት አቅም አለንና? ምንም!

#ዘንድሮስ_አልቀርም! #የአእላፋት_ዝማሬ!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

03 Jan, 06:39


#መርቆሬዎስ_ሆይ፤ ፈጽሞ ለሚያምረው ቁመናህና ደም ግባትን ለተመላ መልክህ ሰላም እላለሁ፡፡ ሥቃዩን ሁሉ የተቀበ ልክ #ሰማዕት_ሆይ፣ ሥዕልህ ተንኮለኛ ዑልያኖስን በገደለው ጊዜ ሀገሪቱ ከሰራዊቱ ጋር በአንድነት ደነገጠች፡፡

#መርቆሬዎስ_ሆይ፤ ሥቃዩን ሁሉ ከፈጸምክ በኋላ በተሳለ ሰይፍ አንገትህ በተቆረጠ ጊዜ ለወጣው ነፍስህ ሰላም እላለሁ፡፡ #ሰማዕት_ሆይ፤ እግረ ልቦናዬ በፊትህ በቆመ ጊዜ በነጋ በነጋ ጎብኘኝ፤ ሰላምንም ስጠኝ፡፡ ደግ እናትና አባት አድርጌሀለሁና፡፡

(መልክአ መርቆሬዎስ)
#በረከቱ_ይደርብን_ጸሎቱ_ትራዳን!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

03 Jan, 05:30


#ከውሻ_ጋር_ከመታገል

ውሾች የሚመላለሱበት ምክንያት የታወቀ ነው። ልክስክስ ሥጋ ወዳለበት አዘውትረው ይገሠግሣሉ። ቀጠሮ ያላቸው ይመስል የሞተ ነገር ባለበት አካባቢ አይታጡም። ታዲያ የውሾችን ምልልስ ለመግታት ምን ማድረግ ይሻላል? ዓይንን ሳይከድኑ መጠበቅ?
እሱማ እንዴት ይሆናል ከመላእክት አንዱ መጥቶ ካልጠበቀልን።
በትር ይዞ መምታት ማስፈራራት ?
እሱም አያዋጣም በትሩን እንደምንም የማይቆጥር ጩኸታችንን የማይሰማ ውሻ ሊያጋጥም ይችላላ!
ታዲያ ምን ይሻላል?
ቀላሉ ዘዴ ከውሻ ጋር ከመታገል የሞተውን ነገር አንስቶ መቅበር ነው። ካጠገብ ማራቅ ነው።

አጋንንት እንደ ውሻ ተመላላሾች ናቸው። በምን እንመልሳቸዋለን? የሞተ ነገር ያዩበትን የልቡና ሜዳ እንደፈለጉ ይፈነጩበታል።
ወንድሜ ሆይ! አጋንንትን እና ውሻን ቁጭ ብለህ ጠብቀህ አታመልጥም። እነሱ የማያንቀላፉ ዘወትር ያንተን መዘንጋት፣ ያንተን መተኛት ሲጠባበቁ የሚኖሩ ናቸው።
በበትር ማለትም በጸሎት በአገልግሎት እመልሳቸዋለሁ ብለህም ከሆነ አንዳንድ ጊዜ በትር እንደማይመልሰው ክፉ ውሻ በጸሎት በጠበል ቢባሉ ማይወጡ አጋንንት አሉ።
በቀላሉ ለማባረር ከፈለግህ ባጠገብህ ያለውን የሞተ ሕይወት መቅበር ነው።

ነፍስ የተለየው በድን ይዘህ እየዞርህ አንተ ባለህበት አካባቢ ሁሉ አጋንንት ይረባረባሉ።
ከውሻ ጋር ከመታገል ውሾችን ሊጠራቸው የሚችለውን ጥምብ ነገር አርቆ መጣል።
የሞተ ክርስትና ይዞ እየዞሩ ሰይጣን ተፈታተነኝ አይባልም። የታወቀ ነዋ! የሞተ እንስሳ ካለ ውሾች አሞሮች ይጠፋሉ?
ሽታው አይደል የሚሰበስባቸው?
እንደዚሁ ሰይጣንስ በበጎ ሥራ መጥፋት ምክንያት የሞተ ክርስትና ካላቸው ሰዎች ዘንድ ማንም ሳይነግረው ያንዣብባል።
ምንም እንኳን ከእግዚአብሔር አጠገብ ቢቀመጥም ሰይጣን ከይሁዳ ልብ እንዴት ሊርቅ ይችላል?
አይቷላ የሞተች ነፍስ።
ብታባርሩትም ይመለሳል።
አይገርምም ግን?
የሚሻለው ምንድነው ካላችሁኝ ሰይጣንን ሊጠራ የሚችል ርኩስ ነገርን ካጠገባችን ማራቅ ነው።

የሞተ እንስሳ ቤተ መንግሥት ውስጥ ቢኖር አሞሮችን ከመሰብሰብ የሚከለክላቸው ማነው? ቤተ መንግሥትም ሆነ ቄራ የሞተ እንስሳ ካለ ለውሾችና ላሞሮች አንድ ነው።
አጋንንትም እንዲሁ ናቸው።
ቤተክርስቲያንም ውስጥ ብንኖር ገዳምሞ ብንደበቅ የሞተ ነገር በውስጣችን ካገኙብን ያችን እያሸተቱ ይዞሩናል።
የሚሻለው ርኩስ የሆነውን አውጥቶ መጣል ነው።

#በሊቀ_ሊቃውንት_ስምዓኮነ_መልአክ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

02 Jan, 01:49


#ለካስ_አባታችሁ_መቅደሱን_አጥነው_እየጠበቋችሁ_ነበር !!!

....ከዓመታት በፊት በታኅሣሥ ሃያ አራት የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓልን ለማክበር በግብጽ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተሰባስበው ቁስቋም ወዳለው የጻድቁ ቤተ መቅደስ በሌሊት ይደርሳሉ።

በስፍራው እንደደረሱም ከበሮ ይዘው « የኢቲሳ አንበሳ ተክልዬ ተነሣ» እያሉ እየዘመሩ በዛፎች እስከተከበበው እጅግ ሰፊው የገዳሙ ግቢ የውስጠኛ ክፍል ድረስ የጻድቁ አባታቸውን ስም እየጠሩ ገሠገሡ።

ይህንን የተመለከቱ የገዳሙ አባቶች በደስታ ተውጠው ሲመለከቱ አንድ አባት ግን እየተንሰቀሰቁ ያለቅሱ ጀመር እኚህ አባት የተክለ ሃይማኖት መቅደስ ያለበትን ቤተ ክርስቲያን ቁልፍ የሚይዙ መነኩሴ ናቸው።

የሚዘምሩትን ወጣቶች እያዩ በመደሰት ፈንታ ዕንባቸውን ለመግታት አልቻሉም ሁኔታው ግራ ያጋባቸው ኢትዮጵያውያኑ ወጣቶች ዝማሬአቸውን ገታ አድርገው እኚህን አባት ቀርበው የለቅሷቸውን ምክንያት ለመጠየቅ ተገደዱ።

መነኩሴውም እንዲህ ሲሉ ከዕንባ ጋር ነገሯቸው።

ትናንት ማታ ከሠርክ ጸሎት በኋላ እንደተለመደው ቤተ ክርስቲያኑን ልቆልፍ ስል ከተክለ ሃይማኖት መቅደስ ውስጥ ጢስ ሲወጣ ተመለከትሁ ምናልባት የሚነድ ነገር ይኖር ይሆናል ብዬ ወደ ውስጥ ስገባ መቅደሱ በዕጣን ጢስ ተሞልቷል።

ምንም የሚነድ ነገር ግን የለም በነገሩ ተገርሜ ቤተ ክርስቲያኑን ቆልፌ ሔድኩ ለካስ አባታችሁ እናንተ ዛሬ እንደምትመጡ አውቀው መቅደሱን አጥነው እየጠበቋችሁ ነበር !! አሏቸው።

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ከመላእክት ጋር የዘመረ ቅዱስ ያሬድን ከካህናተ ሰማይ ጋር ያጠነ ተክለ ሃይማኖትን ያፈራች ቤተክርስቲያን ናት።

#ከግዮን_ወንዝ_መጽሐፍ_የተወሰደ

#እንኳን_ለበዓለ_ልደተ_ተክለ_ሃይማኖት_አደረሳችሁ
#የጻድቁ_በረከት_ይደርብን_ጸሎታቸዉ_ትራዳን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

31 Dec, 06:58


ታኅሣሥ ፳፪ (በዓለ ደቅስዮስ ) ብሥራተ ገብርኤል ይባላል

በዚህችም ዕለት እመቤታችንን ድንግል ማርያምን የከበረ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በአበሠራት መሠረት ደቅስዮስ በዓልን አደረገ፡፡

ደቅስዮስ የተባለው ኤጲስ ቆጶስ ከፍቅሩ ጽናት የተነሳ የተአምራቷን መጽሐፍ ሰብስቦ ያዘጋጀ ነው፡፡ መጽሐፉን ስለጻፍክ ብላ እመቤታቸን ደስ መሰኝቷን ነግራው ተሰውራለች ይህንን በራዕይ ባየ ጊዜ የእርሷን ክብር አብዝቶ ይጨምር ዘንድ አሰበ ሰዎችም አስበውት የማያውቁትን የቅዱሰ ገብርኤል ብሥራት በዓሏን አከበረ ሰዎችም እጅግ ተደሰው በዓሉን በታላቅ ድምቀት አከበሩት ይህችም በዓል በጵጵስናው ዘመን ተሠርታ እስከ አሁን ስትከበር ኖራለች፡፡
እመቤታችን ለቅዱስ ደቅስዮስ ዳግመኛ በተገለጸችበት ጊዜ የከበረ ልብስ ይዛ ፤ ደቅስዮስ ሆይ ስለ አከበርከኝ ደስ አለኝ እኔም ዋጋህን ልከፍልኽ መጣሁ ይህችን ልብስ ልበስ በላዩም ትቀመጥ ዘንድ ወንበር አመጣሁልህ ከሰው ወገን ይህን ልብስ ሊለብስ እና እዚህ ወንበር ላይ ሊቀመጥ ከቶ የሚችል የለም ደቅስዮስም ካረፈ በኃላ ሊለብሱ እና ሊቀመጡ የነበሩ በመሞታችው በዙኃን የእመቤታችንን ተአምር አይተው አደነቁ

#የብሥራቱም_ነገር_እንዲህ_ነው

እመቤታችን ያን የተጠማ ውሻ ውኃ ባጠጣችው ጊዜ ፤ በዚህ ዘመን አምላክ ከድንግል ይወለዳል ያላት ካንቺ ይሆን እያሉ ይዘባበቱባት ነበር ደናግለ ፳ኤል ወዲያውኑ ከኋላዋ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ትጸንሲ አላት ዞር ብትል አጣቸው አባቴ አዳምን እና እናቴ ሔዋንን ያሳተ ጠላት ይሆናል ብላ ዝም ብላ ሄደች ዳግመኛም ቤት ከደረሰች በኋላ ትጸንሲ አላት ይህ ነገር ተደጋገመ ብላ ወደ ቤተ መቅደስ ነገሩን ልትረዳ ሄደች በወርቅ ወንበሯ ተቀምጣ ከደናግለ ፳ኤል ጋር የተካፈለችውን ሐር እና ወርቅ እያስማማች ስትፈትል ቅዱስ ገብርኤል ተገልጾ:-
‹‹#ተፈሥሒ_ፍሥሕት_ኦ_ምልዕተ_ጸጋ ›› ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበለሽ አላት ሉቃ፡፩፥፳፰ ይህን ሰምታ በደነገጠችም ጊዜ
‹‹#ኢትፍርሂ_ማርያም_እስመ_ረከብኪ_ሞገሰ_በኀበ_እግዚአብሔር ›› በእግዚአብሔር አብ ዘንድ ባለሟልነትን አግኝተሻል አትፍሪ እነሆ ትጸንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ እግዚአብሔርም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል ለመንግሥቱም ፍጻሜ የለውም አላት ሉቃ፡፩፥፴-፴፪ ……ይህ ነገር እንደምን ይሆንልኛል አለችው <<#መንፈስ_ቅዱስ_ይመጽእ_ላዕሌኪ_ወኃይለ_ልዑል_ይጼልለኪ›› መንፈስ ቅዱስ ባንቺ ላይ ይመጣል የልዑል ኃይልም ይጋርድሻል ብሎ የተቀመጠችበትን የወንበሩን እጀታ አለምልሞ ይህን ማን አደረገው ቢላት እግዚአብሔር አለችው፡፡ ይህንንም የሚያደርግ እግዚአብሔር ነው ‹‹#አስመ_አልቦ_ነገር_ዘይሰአኖ>> የሚሳነው የለምና ኤልሳቤጥ እንኳን ጸነሰች ይህ ስድስተኛው ወር ነው አላት ፡፡
ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ ‹‹ እንደቃልህ ይሁንልኝ ይደረግልኝ ›› አለችው፡፡ ይህን ቃሏን ምክንያት አድርጎ ወልድ ዋኅድ እግዚአብሔር በማኀፀኗ አደረ። ሉቃ፡፩፥፳፮-፴፰
ይህ የሆነው መጋቢት ፳፱ ቀን ነው ታኅሣሥ ፳፪ እንዲከበር ያደረገው ግን ከላይ እንደገለጽነው ኤጲስ ቆጶሱ ቅዱስ ደቅስዮስ ነው ፡፡ መጋቢት ፳፱ በጾም ምክንያት በሚገባ አይከበርም ነበርና ከበዓለ ልደቱ ሰባት ቀን አስቀድሞ ታኅሣሥ ፳፪ በታላቅ ድምቀት እንዲከበር ሆኗል፡፡

እንኳን አደረሳችሁ
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

30 Dec, 06:45


የሰላምን ንጉሥ ወልዳ የሰጠች ሰላሟ የማይናጋ ደኅንነቷ የማያሰጋ የሰላም ከተማ አማናዊቷ ኢየሩሳሌም ድንግል ማርያም ናት ስለዚህ የንጉሥ ዙፋን በወርቅ በልዩ ልዩ ጌጣጌጥ እና በከበሩ አልባሳት እንደሚያሸበርቅ ሁሉ እመቤታችንም የሰማያዊው ንጉሥ ዙፋን በመሆኗ በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ በቅድስና የተጌጠች በንጽሕና ያሸበረቀች በሕብረ ዜማ የተመሰገነች ዘላለማዊ ድንግል ናትና ።

ድንግል : ሆይ : ባንቺ : ዓለም : ዳነ : በልጅሽም : ሰላም : ሆነ

በረከቷ ይደርብን አማላጅነቷ አይለየን!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

28 Dec, 07:54


#ይሄን_ያደረገው_ቅዱስ_ገብርኤል_ነው

ሶስቱ ወጣቶች ለጣኦት አንሰግድም ብለው በገመድ ታስረው ወደ ገደል በነደደው እሳት ውስጥ በተጣሉ ጊዜ እሳቱ ያበርደው ዘንድ ከእግዚአብሔር ተልዕኮ መጥቶ የነደደውን እሳት ወደ ውኃነት የለወጠላቸው #የመላዕክት_አለቃ_ቅዱስ_ገብርኤል_ነው ።

ንጉሡ ናቡከደነጾርም ወደ እሳቱ ውስጥ ቢመለከት ወደ እሳቱ ያስጣላቸው ሦስቱ ወጣቶች እሳቱ ስይነካቸው ሳይገድላቸው ይልቁንም ከሦስት በልጠው አራት ሆነው አያቸውና እንዲህ ብሎም ተናገረ « አራተኛውም የእግዚአብሔር ልጅ ይመስላም » ብሎ አለ ። ይህም ማነው #ቅዱስ_ገብርኤል_ነው ።

#ቅዱስ_ገብርኤል የሶምሶምን ፅንስ ያበሰረ
#ቅዱስ_ገብርኤል ለዳንኤል ምስጢር የተረጎመ
#ቅዱስ_ገብርኤል ለአጋር በምድረበዳ ውኃን ያፈለቀ
#ቅዱስ_ገብርኤል ዲያብሎስ መላእክትን ባወከ ጊዜ ያረጋጋ
#ቅዱስ_ገብርኤል በእባብና በጊንጦች ላይ የተሾመ ባለ ጸጋ መልአክ ነው።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

28 Dec, 05:34


“ተቤዥቼሀለሁና አትፍራ አንተ የኔ ነህ በውሃ ውስጥ በምታልፍበት ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ ወንዙን ስትሻገር አያሰጥምህም በእሳት ውስጥ ስትሄድ አያቃጥልህም ነበልባሉም አይፈጅህም" ኢሳ 43:3

የእግዚአብሔር ባርያዎች የሆኑት አናንያ አዛርያ ሚሳኤል በተማረኩበት ሀገር ሆነው ለእግዚአብሔር በመታመናቸው ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ የእሳቱን ኃይል አጥፍቶላቸዋል አሁንም ቸሩ አምላካችን በምድራችን ላይ የነደደውን የዘረኝነት የመለያየት የመገዳደል ያለመደማመጥና ያለመከባበር እንዲሁም ያለመዋደድ እሳት ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ ያጠፋልን ዘንድ የመልአኩ አማላጅነትና ጠባቂነት ዘወትር ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓለ ክብር አደረሰን አደረሳችሁ።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Dec, 05:44


#ሰማዕቱ_ቅዱስ_እስጢፋኖስ

በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በሰማዕቱ ስም ለምናመሰግንበት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ ወርኀዊ መታሠቢያ ክብረ በዓል እንኳን አደረሰን።

የትውልድ ሀገሩ #ኢየሩሳሌም ሲሆን አባቱ #ስምዖን እናቱ ደግሞ #ማርያም ይባላሉ ዘመኑም የመጀመርያው ምእተ ዓመት ነው

እንግዲህ በዘመነ ሐዋርያት የማዕዱን እና የውስጡን አገልግሎት እንዲያስተናብሩ መንፈስ እና ጥበብ የሞላባቸው ሰባት ሰዎች ተመርጠው በሐዋርያት አንብሮተ ዕድ ከተሾሙት ሰባቱ ዲያቆናት መካከል በቅድስና ሕይወቱ ለክርስቲያኖች አብነት የሆነው ሰማዕቱ #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ይገኝበታል እስጢፋኖስ የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም #አክሊል ማለት ነው።

መጽሐፍ ቅዱስን ወደ ግእዝ በኋላም ወደ አማርኛ የመለሱት አባቶች በቀጥታ የግሪኩን እስጢፋኖስ የሚለውን ቃል ተጠቅመዋል #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ምንም እንኳን ስሙ የግሪክ ስም ይሁን እንጂ በትውልዱ አይሁዳዊ ነው።

ወላጆቹ ይህንን ስም የሰጡት ተብሎ የሚታመነዉ ወላጆቹ በፍልስጤም ጠረፋማ ከተሞች ይኖሩ ስለ ነበር የግሪክ ባሕልና ቋንቋ ተጽእኖ አድሮባቸው ይሆናል ተብሎ ይገመታል።

#ቅዱስ_እስጢፋኖስ በሐዋርያት ጥበቃ የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ከአምላክ ዘንድ ባገኘው የማስተማርና የፈውስ ሀብት ያገለግል ነበር በእርሱም ታላላቅ ተአምራት ይፈፀሙ ነበር።

ስለዚህም ሕዝቡ ከፊት ይልቅ እጅግ እየበዛና በትምህርት እየጠነከረ መጣ አይሁድም ይህን ተመልክተው በቅዱስ #እስጢፋኖስ ላይ በቅናትና በጠላትነት ተነሡበት ነገር ግን ከመንፈስ ቅዱስ ባገኘው ጥበብና ኃይል እነርሱን በቃልም በድርጊትም ይቃወማቸው ነበርና ሊረቱት አልተቻላቸውም።

ስለዚህም #እግዚአብሔርን ሙሴን ሲሳደብ ሰምተነዋል ሙሴ የሠራልንን ሥርዐት ይለውጣል በዚህ ቤተ መቅደስና በሕጉ ላይ የስድብን ቃል ይናገራል ይህንንም ቤተ መቅደስ የናዝሬቱ ኢየሱስ አፍርሱ ብሏል እያለ ያስተምራል እያሉ ሕዝቡን ሽማግሌዎችንና ጸሐፍትን በማናደድ ይዘው ከሸንጎ ፊት አቆሙት

ቅዱስ #እስጢፋኖስን በሸንጎ ፊት ባቆሙት ጊዜም ፊቱ ልክ እንደ #መልአክ ፊት ሆኖ በርቶ ነበር እርሱም ለተከሰሰበት ነጥብ መልስ ሰጠ ከአብርሃም እስከ ክርስቶስ ለእነርሱ የተሰጣቸውን በረከት በመቃወማቸው ከተስፋ ቃል እርቀው እንደተወገዱ ገለጠላቸው።

#ክርስቶስንም ባለመቀበላቸው ወቀሳቸው በዚህም ምክንያት በቁጣ ተነሣስተው ከከተማ ውጭ በመውሰድ በድንጋይ ወግረው ገደሉት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ አይሁድ በድንጋይ እየወገሩት ሳለ ሰማያት ተከፍተው #ክርስቶስን በአብ ቀኝ ቆሞ ተመለከተ ይህንን ራእይ የክርስቶስን ትንሣኤ ለማይቀበሉት አይሁድ አሰምቶ ተናገረ።

እነርሱ ከፊት ይልቅ በእርሱ ጨከኑ በድንጋይም ወገሩት ነገር ግን #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ጌታውን ክርስቶስን መስሎ ነበርና ልክ እንደ መምህሩ #አቤቱ_ይህን_ኃጢአት_አትቁጠርባቸው” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ሰጠ በቤተክርስቲያንም ታሪክ ስለ ክርስቶስ መስክሮ ሰማዕትነትን የተቀበለ የመጀመሪያው ሰማዕት ሆኗል።

በደማስቆ መንገድ ላይ ክርስቲያኖችን ያሳድድ የነበረ ሳውል በኋላም ቅዱስ ጳውሎስ ተብሎ ስያሜ የተሰጠው ሐዋርያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ በሚወግሩበት ወቅት በእርሱ ሞት ተስማምቶና ድንጋይን በእስጢፋኖስ ላይ ያነሡትን የአይሁድ ልብስ ይጠብቅ የነበረ ብላቴና ነበር

ነገር ግን #ቅዱስ_ጳውሎስ ሐዋርያ ከሆነ በኋላ የሰማዕቱ #የእስጢፋኖስን ቤተሰቦች አጥምቋቸዋል ይህ ደግሞ ድንቅ ነው የሰማዕቱ መታሠቢያ በቤተክርስቲያን መጽሐፈ ስንክሳር የበዓላት ዝርዝር ላይ ቀን ተሰጥቶት ይከበራል ይኽም

በመስከረም 17 በዓለ ፍልሰተ አጽሙ፤ ጥቅምት 17 ቀን የዲቍና ማዕረግን በአንብሮተ ዕድ በሐዋርያት የተቀበለበት፤ ጥር 1 ደግሞ የልደቱ እና የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆኖ ይከበራል በየወሩ በ 17 የሰማዕቱ መታሠቢያም ነው።

#በረከቱ_ምልጃና_ጸሎቱ_አይለየን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Dec, 04:57


#ቀዳሜ_ሰማዕት_ቅዱስ_እስጢፋኖስ

እንኳን ለሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ እስጢፋኖስ ወርኀዊ የመታሰቢያ በዓሰ በሰላም አደረሰን!!!

በሐዲስ ኪዳን በክርስትና ምክንያት ሰማዕትነትን ከተቀበሉ መካከል የቀደመ፣ ክብር፣ ቅዱስ ሰማዕት

በመጽሐፍት እውቀቱ የተለየ በመንፈስ ቅዱስ የተቃኘ ሊቀ ዲያቆናት

በከሳሾቹ ፊት ሞትን ሳይፈራ የክርስቶስን እውነት የመሰከረ፣ በብርሃን የተመላለሰ ሐዋርያ

ልክ እንደ ክርስቶስ ጠላቶቹ በሀሰት ክስ ተነስተው ሲገድሉት ይቅርታን የለመነላቸው ቅዱስ

ታላቅ ሐዋርያ፣ ሰባኪ፣ ጻድቅ፣ ሰማዕት የሆነው ቅዱስ እስጢፋኖስ በዚህ ቀን በየወሩ ይታሰባል

የሊቀ ዲያቆናት ወቀዳሜ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስ ምልጃና በረከት ይደርብን።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

25 Dec, 10:38


#አቻ_የሌለው_ርኅርኂተ_ልብ_እመ_ምሕረት

እመቤታችን ከቤተ ዮሴፍ ሳለች ከዕለታት በአንዱ ቀን ገንቦዋን አዝላ ውኃ ልትቀዳ ወደ ወንዝ በሔደች ጊዜ የተጠማ ውሻ ውኃን ፈልጎ መጣ በወንዙ አካባቢ ውኃን ሲቀዱ የነበሩ ሴቶች ግን ያን በውኃ ጥም የተቃጠለውን ውሻ አባረው ደብድበው ሰደዱት፡፡

« ምነው አታጠጡትም እሱስ የእግዚአብሔር ፍጡር አይደለም ? አለቻቸው እመቤታችን አንቺ ሥራ ፈቲቱ አጠጪው እንጂ እኛስ ለባሎቻችን ለልጆቻችን እናስባለን ፤ በዚያውስ ላይ እንዲህ ያለውን ርኅራኄ ከወዴት አገኘሽው አምላክ ይወለዳል የሚባለው ካንቺ ይሆን ብለው ተዘባበቱባት።

በዚያን ወራት ማርያም ከምትባል አምላክ ይወለዳል እየተባለ ትንቢት ይነገር ነበርና ነው እመቤታችንም ዕቃዋን እንዳያረክስባት በወርቅ ጫማዋ ከገንቦዋ ቀድታ አጠጥታዋለች ምክንያቱም እርሷ ርኅርኂተ ልብ ናትና ነው።

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታቱ ላይ ‹‹ እመቤቴ ሆይ ! ለተጠማው ውሻ ራርተሸ ውኃን እንዳጠጣሽው ድንቅ በሆነው ርኀራኄሽ አስቢኝ » በማለት አቻ የሌለው ርኅራኄዋን ተማጽኗል።

እመቤታችን ውሻውን ስታጠጣው የዕብራውያን ሴቶች እንዲህ ሲሉ ይገዳደሯት ነበር ‹‹ ማድጋሽን አጎደልሺው ቀድቼ እሞለዋለሁ እንዳትይ ውኃው የጉድጓድ ውኃ ነው መቅጃ የለሽም›› አሏት።

እመቤታችንም የምሥጢር መዝገብ ናትና ‹‹ ውኃ የሚገኘው ከላይ ነው እንጂ ከታች ነውን ? ይህን ውኃ የፈጠረ ይሰጠኛል ። ›› ስትል ነገረ እግዚአብሔርን በማዘከር መልስ ሰጠች ያንጊዜ ገንቧዋ በተአምራት ሞልቶላታል፡፡

#ድንግል_ለምኝልን_ኀጢአታችን_በዝቷል_ልብሽ_እንኳን_ለኛ_ለውሻ_ራርቷል!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

24 Dec, 09:12


#ቅዱስ_ሚናስ_ሰማዕት

ወር በገባ በ15 የሰማዕነት ክብሩ እንደ ሰማዕታት አለቃቸው እንደ ጊዮርጊስ
የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ሚናስ ወርሐዊ መታሰቢያው ነዉ፡፡ ሚናስ ሆይ በግብረ መንፈስ ቅዱስ ለተዋሐደ ክርስቶስ ለተባለ ለእግዚአብሔር በሕጉ ሰሌዳ ላይ ለተቀረጸ ስም አጠራርህ ሰላምታ ይገባል፡፡

ሚናስ ሆይ ለራስህ ሁለተኛ ለሚሆን ለራስ ጸጉርህ ሰላምታ ይገባል፡፡
ሚናስ ሆይ እንደ አጥቢያ ኮከብ ለሚሆን አይኖችህና፤ ለአይኖችህ ቅንድቦች
ሰላምታ ይገባል፡፡
ሚናስ ሆይ ቅላቱ ከሮማን ቅላት ለሚቀሉ ጉንጮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡
]ሚናስ ሆይ በእየለቱ ስድብን ላልተናገሩ ከንፈሮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡
ሚናስ ሆይ ከሰባቱ ሊቃነ መላዕክት ጋር ከሥላሴ ፊት ቆሞ ምስጋናን
ላላቋረጡ አንደበትህ ሰላምታ ይገባል፡፡
ሚናስ ሆይ ከሮም ሰዎች ወይን ጣዕም ለራቀ ጉሮሮህ ሰላምታ ይገባል፡፡
የሰላም ሰው እንደሆነ እንደ ሰማዕቱ መርቆሬዎስ መከራን የታገስክ ሚናስ ሆይ
ሰላምታ ይገባል፡፡
የጊወርጊስ ወገን ሰማዕት ሚናስ ሆይ አስቀድሞ የሕዝቡ የምዕመናን
መምሕር ሦስት ቀን እንደተሰወረ ከፀብና ከጥፋት የኢትያጵያ ህዝብ ሰውራቸው፡፡
ሚናስ ሆይ ሥላሴን ሲያመሰግን ምስክርነትንና ገድልን እንደ ዝናር
ለታጠቀ፤ወገብኅና እንብርትኅ ሰላምታ ይገባል፡፡
ሚናስ ሆይ በመንግሰተ ሰማይ ከተሰበሰቡ ሰማዕታት ጋር የማያልቅ ተድላ
ነፍስን ታደርግ ዘንድ ከስጋህ ለተለች ነፍስህ ሰላምታ ይገባል፡፡
ሚናስ ሆይ ለሥጋህ በድንና በበፍታ ለሚሆን ግንዘትህ ሰላምታ ይገባል፡፡
በዚች በወርሐዊ በዓልህ ዝክርህን እና መታሰቢያህን ያደረጉ ከመከራ ከጥፋት
ሁሉ አድናቸው፡፡
(መልክአ ቅዱስ ሚናስ)

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

24 Dec, 06:56


#ዘመን_ሲረዝም_ጸሎት_ያልተሰማ_ይመስላል።

ሰይጣን ሰዎችን ከሚጎዳበት ክፋቱ አንዱ ለሰዎች ኃጢአተኛ እንደ ሆኑ በመንገር ነው ኃጢአቱን ሲጀምሩ ኃጢአቱን ቀላል ያስመስላቸዋል።

ቆይቶ ኃጢአተኛ እንደ ሆኑ የሚነግራቸው ደግሞ ንሰሐ እንዲገቡ ሳይሆን ኃጢአተኛ ስለ ሆኑ እግዚአብሔር አይወደኝም እንዲሉ ነው፡፡

እግዚአብሔር ስለማይወደኝም ብለው መልሰው በቀቢጸ ተስፋ ኃጢአትን እየለመዱ ከእርሱ ጋር እንዲኖሩ ነው፡፡

ይሁን እንጂ የዘካርያስ ጸሎት በትዕግሥቱ በንጹሕ ክህነቱ እንደ ተሰማለት የሕዝቡም ኃጢአተኛ መሆን በእርሱ ጽድቅና ጸሎት እንዲሁም መሥዋዕት ይደመሰሳልና ቆመን ዘካርያስን መጠበቃችንን አንተው፡፡

ዘካርያስ ዘመኑን በሙሉ ቅዱስ ገብርኤል እስኪገለጥለት በመቅደስ እንደኖረ ካህናትም የአምላካቸውን ፊት እስኪያዩ ልጅ ቢያጡም ቢራቡም ቢቸገሩም ቢገፉም ከአባታቸው መቅደስ ግን አይወጡም፡፡

ዘካርያስ ቢዘገይም እኛ ኦርቶዶክሳውያን ግን ዘካርያስ ካህን ከቤተ መቅደስ እስኪወጣ ዙሪያውን መቆማችንን አንተው ቅዱስ ገብርኤልም ምንም ዘመኑ ቢረዝምም መገለጡ አይቀርምና፡፡

ጸሎት ልመናችን ምንም ቢዘገይብን ምንም ቶሎ ባይደረግልን ከአባቶቻችን ከካህናት አንለይ ዘካርያስ ካህን ዲዳ ቢሆንም ከዘጠኝ ወር በኋላ ግን በልጁ ልደት እግዚአብሔር አምላክ ዲዳ አንደበቱን እንዲናገር አድርጎታልና።

ለመፍትሔዎቻችን ካህናት ቶሎ መልስ ባይሰጡንም እንደ ዲዳ ዘካርያስ ዝም ያሉን ቢመስሉንም በጊዜው ግን ለደስታ ቀን ያበቁናልና ከካህናት እጅ እየራቅን አውሬ አይብላን።

በዘካርያስ ጸሎት ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል እንደ ተገኘለት ዛሬም ያለጥርጥር በቅን የሚጸልይ ከሱራፌል ከኪሩቤል ጋር አብሮ እንደሚቆም ልብ ይሏል።

#እግዚአብሔር_በአባቶቻችን_ጸሎት_ይማረን!
#እነ_ቅዱስ_ገርኤልን_ልኮ_ጸሎትህ/ሽ #ተሰማልህ/ሽ #ደስ_ይበልህ/ሽ #ይበለን!


#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

23 Dec, 09:28


#አቡነ_አረጋዊ_ጻድቅ

#በምድር_መንነሃልና_በደስታ_ከዚህ_ዓለም_ድካም_አሳርፍሃለሁ

#ጻድቁ_አባታችን_አቡነ_አረጋዊ_ጥቅምት_14_ቀን በ 99 ዕድሜያቸው በጾም በጸሎት በተጋድሎ ከኖሩበት ገዳም በእግዚብሔር ጸጋ እንደ ሔኖክና እንደ ኤልያስ ከሞት ገጽ የተሠወሩበት ዓመታዊ የመታሰቢያ ቀናቸው ነው ።

ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ መንፈሳዊ አገልግሎት ካበረከቱ ቅዱሳን አባቶች መካከል አንዱ ጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ናቸው ።

የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የማይዘነጋ ዘለዓለማዊና ሰማያዊ ውለታቸውን አስባ ፤ በስማቸው ጽላት ቀርጻ ፤ ቤተ ክርስቲያን ሰይማ ፤ ገድላቸውንና ተአምራታቸውን ጽፋ ቅዱስ ብላ ታከብራቸዋለች ።

በየወሩና በየዓመቱ ዕረፍታቸውን ( ዕርገታቸውን ) ታዘክራለች ! በቃል ኪዳናቸውና በስማቸውም ፈጣሪዋን ትማጸናለች ።

ጻድቁ አቡነ አረጋዊ በ5ኛው ክፍለ ዘመን ( 460 ዓ.ም ) በመንግሥተ አልአሜዳ የሮማ ግዛት ከሆኑት ከሶርያና ከቁስጥንጥንያ እንዲሁም ከተለያዩ ሀገሮች ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት ዘጠኝ ቅዱሳን አንዱ ናቸው ።

እነዚህን ስምንቱን ቅዱሳንን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ መንገድ የመሯቸው እኚህ ጻድቅ አባት ናቸው ዘጠኙ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ የመጡበት ዐቢይ ምክንያት በጉባዔ ኬልቄዶን በ451 ዓ.ም መለካውያን ባነሡት የክሕደት አመፅ የኹለት ባሕርይ እምነት አንቀበልም በማለታቸው የቢዛንታይን መንግሥት የቁም ስቃይ ስላጸናበቸው ነበር ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ ‹‹ ከአንዱ ሀገር ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላው ሽሹ ›› ያለውን መለኮታዊ ቃል ተገንዝበው በእምነትና በአምልኮት ወደሚመስሏቸው ሀገራት ጥግ ፍለጋ ተሰደዋል ።

አቡነ አረጋዊ በትውልድ ሀገር ሮማዊ ናቸው አባታቸው በሮም ከነገሡ ነገሥታት አንዱ ሲሆኑ ስማቸውም ‹ ይስሐቅ › ይባላል ፤ እናታቸው
‹ አድና › ይባላሉ እግዘአብሔርን የሚፈሩ በማኅበረሰባቸው ዘንድ የተከበሩ ነበሩ ።

አቡነ አረጋዊ ከመምህራቸው ከአባ ጳኩሚስ ዘንድ ሥርዓተ ማኅበርን እንዲሁም ሥርዓተ ምንኵስናንና ተምረው ገዳማዊ ሕይወትን ከመሠረቱት ከአባ እንጦንስ በአራተኛ ደረጃ የሚታወቁ ታላቅ አባት ናቸው ።

አቡነ አረጋዊ ሦስት ስሞች አላቸው ! አንደኛው ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ‹‹ ገብረ አምላክ ›› የሚለው ነው ! ኹለተኛው መምህራቸው አባ ጳኩሚስ ያወጡላቸው የምንኩስና ስማቸው ‹‹ ዘሚካኤል ›› የሚለው ነው ።

ሦስተኛው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ስምንቱ አኀው ‹‹ አረጋዊ ›› የሚለው ስም ሲሆን በኢትዮጵያ መጠሪያ ስማቸው ሆኖ ቀርቷል ።

እነዚህ ዘጠኝ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአት መሥርተው ገዳማትን አቅንተው ወንጌልን ሰብከዋል ሥርዓተ ምንኩስናንና ገዳማዊ ሕይወትን አስተምረዋል ።

ከገድላቸው መካከል ጎልቶ የሚታወቀው በቅዱስ ሚካኤል ተራዳዒነት በዘንዶ ኀይል ደብረ ዳሞን ተራራ ወጥተው መኖራቸው ነው ።

ይህም የዘንዶውን ጅራት በመያዝ ከደብረ ዳሞ ተራራ ላይ ወጥተው በዚያ ፍጹም ተጋድሎ ፈጽመዋል ፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ስማቸውን ለሚጠራ መታሰቢያቸውንም ለሚያደርግ ሁሉ ምሕረትን እንደሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው ጥቅምት 14 ቀን በ 99 ዕድሜያቸው በጾም በጸሎት በተጋድሎ ከኖሩበት ገዳም በእግዚብሔር ጸጋ እንደ ሔኖክና እንደ ኤልያስ ከሞት ገጽ ተሠውረዋል

በመጨረሻም ‹‹ መንፈስ ቅዱስ ከሰማይ መጣ ፤ ጸሎትህን ሰምቻለሁ ፤ ብዙ የሆነ ትዕግሥትህን አይቻለሁ ፤ ድውያንን ትፈውስ ዘንድ ስልጣን ሰጥቼሃለሁ የታመሙት ሁሉ ይድናሉ ፤ ለምጻሞች በቃልህ ይነጻሉ ፤ በምድር መንነሃልና እነሆ በደስታ ከዚህ ዓለም ድካም አሳርፍሃለሁ ወደ ዘለዓለም ሕይወት ትሔዳለህ ። ›› ብሏቸው ከዐይነ ሞት ተሠወሩ ።

ቸር የዋህ እግዚአብሔርን የምትፈራ አባታችን አቡነ አረጋዊ ሆይ ስለእኛ ጸልይ አቤቱ አምላካችን ሆይ አባቶቻችን አንተን ተማመኑ ተማምነውም አዳንካቸው ወደ አንተ ጮኹ ዳኑም አንተንም ተማመኑ አላፈሩም የሰማያትን ሙሽርነትን አስቀድመው ስለአንተ ነፍሳቸውን ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋልና ስለተጋድሏቸውና ስለጽኑዕ እምነታቸው ስትል ማረን ይቅር በለን!



#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

21 Dec, 20:00


ታሕሳስ ፲፪ በካ/ቆ/ደ/ገ ቅዱስ እስጢፋኖስ በቅዱስ ሚካኤል ወርኀዊ መታሰብያ በዓል ማታ ጉባዔ በአውደ ምሕረት የተሰጠ ትምህርት

የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል

መዝ፡ ፴፫፥፯

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

21 Dec, 12:01


#አባ_ሳሙኤል_ዘዋሊ(ዘዋልድባ)

ሃገራችን እልፍ አእላፍ ቅዱሳንን አፍርታለች እንኩዋን በተባረከው በቀደመው ዘመን ይቅርና ዛሬም ከሀገር ተርፈው ለዓለም የሚጸልዩ በየበርሃውና በየገዳማቱ የወደቁ ብዙ አባቶችና እናቶች አሉን በኢትዮጵያ ውስጥ ከተነሱ ቅዱሳን መካከል ሳሙኤሎች ልዩ ቦታ አላቸው በ20 ዓመታት ልዩነት ብቻ 6ቱ ሳሙኤሎች ተነስተው ከቅድስና ሕይወት እስከ ስብከተ ወንጌል ከገዳማዊ ሕይወት እስከ ምናኔ በጐውን ጐዳና አሳይተዋል

እነዚህም
1.ሳሙኤል ዘዋልድባ
2.ሳሙኤል ዘጣሬጣ
3.ሳሙኤል ዘቆየጻ
4.ሳሙኤል ዘግሺ
5.ሳሙኤል ዘሃሌ ሉያ እና
6.ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ናቸው

በተመሳሳይም በግብጽ የደብረ ቀልሞኑን ኮከብ ጨምሮ (መልአኩን ቀውስጦስን ከጌታ ያማለዱት) ብዙ ሳሙኤሎች ተነስተዋል የድሮ እናቶቻችን በእውነት ስም መሰየሙን ይችሉበታል ሳሙኤል ማለት
ሰምዓኒ እግዚአብሔር ስዕለትየ እግዚአብሔር ልመናየን ሰማኝ ማለት ነውና።

ወደ ቀደመ ነገራችን እንመለስና ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ ሳሙኤል ዘዋሊ የተወለዱት በ13ኛው መቶ ክ/ዘመን (በ1295) በምድረ አክሱም ነው ወላጆቻቸውም እስጢፋኖስና ዓመተ ማርያም ይባላሉ የዘር ሐረጋቸው ከካህናት ወገን ነውና ጻድቁ ገና በልጅነት ምሥጢራተ ሃይማኖትን ጠንቅቀዋል ለዚህም ይመስላል ገና ሕጻን ሳሉ ምናኔን የተመኙት።

ከልጅነታቸው ጀምረው ወላጆቻቸውን ያገለገሉት ሳሙኤል ትምህርታቸውን ሲፈጽሙ የተጓዙት ወደ ደብረ በንኮል ነበር
በጊዜውም የጻድቁ ወላጆች ዐርፈው እንደ ነበር ይነገራል ደብረ በንኮል ማለት የታላቁ ኮከብና አበ መነኮሳት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ነው።

መድኃኒነ እግዚእ ለሀገር ብርሃን የሆኑ ቅዱሳንን ያፈሩ ዘንድ ሲተጉ እግዚአብሔር 7ቱን ከዋክብት ሰጣቸው ከእነዚህ መካከልም ቀዳሚው አቡነ ሳሙኤል ናቸው
ቀሪዎቹ ደግሞ

አቡነ ያሳይ ዘመንዳባ
ሳሙኤል ዘጣሬጣ
ሳሙኤል ዘቆየጻና
አቡነ ዮሐንስ ዘጉራንቄ
አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤን
አቡነ ታዴዎስ ዘባልርዋ ናቸው

አቡነ ሳሙኤል ከ6ቱ ባልንጀሮቻቸው ጋር ሆነው በደብረ በንኮል ተጋድሎን ጀመሩ እንጨት ይሰብራሉ፤ ውሃ ይቀዳሉ፤ እህል ይፈጫሉ፤ በፍጹም ልባቸውም ይታዘዛሉ
ጐን ለጐን ደግሞ ከቅዱሱ መምህራቸው ከአባ መድኃኒነ እግዚእ ጽንዓትን፣ ትሕትናን፣ ትሕርምትን፣ ሥርዓተ ገዳምንም ያጠኑ ነበር ከአገልግሎታቸው ማማር የተነሳ ሁሉን ደስ ማሰኘት ቻሉ በዚህ ጊዜም ጻድቁ አባ መድኃኒነ እግዚእ አቡነ ሳሙኤል ዘዋሊንና 6ቱን አበው ጠርተው ለምንኩስና አቀረቧቸው ይገባችዋል! ሲሉም ከአመክሮ ወደ ምንኩስና አሸጋገሯቸው።

በዚያች ቀን 7ቱ ሲመነኩሱ ከሰማይ ብርሃን ወርዶ በመታየቱ ቅዱሳኑ ከዋክብት ብሩሃን ተባሉ ለተወሰነ ጊዜም በዚያው በገዳሙ አገለገሉ የአቡነ ሳሙኤል ዘመዶች ግን እየመጡ ጻድቁን ስላስቸገሩ 7ቱም ቅዱሳን ተመካክረው ከአባታቸው መድኃኒነ እግዚእ ተባርከው ከደብረ በንኮል ወጡ።

ሁሉም መንፈስ ቅዱስ ወደ መራቸው ሲሔዱ 3ቱ (ማለትም ሳሙኤል ዘዋሊ ያሳይ ዘመንዳባና ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤ) ወደ ጣና ሔዱ በዚያም ለጥቂት ጊዜ አብረው ከቆዩ በኋላ ለአገልግሎት ተለያዩ
አቡነ ያሳይ መንዳባን፤ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ጉጉቤን ይዘው እዛው ጣና አካባቢ ሲቀሩ
አባ ሳሙኤል ወደ ዋልድባ ሔዱ።

ዋልድባ በ5ኛው መቶ ክ/ዘመን በጌታ ፈቃድ የተመሠረተ ሲሆን 860ው መሥራች ቅዱሳን በመሠወራቸው እንደ ጠፋ ይቆጠር ነበርና አቡነ ሳሙኤል እንደ ገና አቀኑት ጻድቁ በዋልድባ የመጨረሻውን ትሕርምት ከመያዛቸው በፊት በጊዜው ከፍተኛ የሆነ የወንጌል አገልግሎት ሰጥተዋል ቀጥለውም ኑሯቸውን ከግሩማን አራዊት ጋር አድርገዋል በስዕለ አድኅኖው እንደምናየው ለዘመናት በአንበሳ ጀርባ ላይ ተጭነዋል ጧት ማታም ብዙ ግሩማን አራዊትን እያስከተሉ ለአገልግሎት ደክመዋል ጻድቁ ከትሕርምት ብዛት እህል ትተው የሻገተ ጐመንና መልኩን የለወጠ ውሃን ለቁመተ ሥጋ ይጠቀሙ ነበር።

አንድ ቀንም መድኃኒታችን ክርስቶስ ወደ እርሳቸው መጥቶ ባረካቸው አካላቸውንም በቅዱስ ምራቁ አትቦ ቀባቸው በዚህ ጊዜም ኃይለ መንፈስ ቅዱስን ተመሉ የክርስቶስን ኅማማት እያሰቡም ዕልፍ ጊዜ ይሰግዱ ጀርባቸውን ይገርፉም ነበር እግራቸውን በሰንሰለት አሥረው ይጋደሉ ነበር በዚህ ግብራቸው አጋንንትን አሳፍረው ፈጣሪያቸውን ደስ አሰኙ ከቆይታ በኋላም ዋልድባ በመነኮሳት ተሞላ ደቀ መዛሙርት በዙ ቀዳሚው ግን አባ ዘሩፋኤል ጻድቅ ነው።

አቡነ ሳሙኤል ለድንግል ማርያም ልዩ ፍቅር ነበራቸው ዘወትር ውዳሴዋንና ቅዳሴዋን በተመስጦ ያደርሱ ነበር ፈጽመውም ያመሰግኗት ነበር ይህንን ሲያደርጉ ከመሬት ክንድ ከፍ ብለው ይንሳፈፉ ነበር ተከታዮቻቸው ሲርባቸውም ውኀውን ቅዳሴ ማርያምን እየጸለዩ ሕብስት (እንጀራ) እያደረጉ ይመገቡ ነበር "ሶበ አተቦ ለማይ በቅዳሴኪ እንዘ ይጼሊ ረሰዮ ሕብስተ ሳሙኤል ጽጌ ሃይማኖት ዘሐቅለ ዋሊ
ምሕረተ ወፍትሐ ለተአምርኪ አኀሊ
ስረዪ ኃጢአትየ ወዕጸብየ አቅልሊ
እስመ ኩሎ ገቢረ ማርያም ትክሊ
እንዳለ ሊቁ" ማኅሌተ ጽጌ

እመ አምላክ ስለ ፍቅር ሰማያዊ ሕብስትን መገበቻቸው ንጹሕ ዕጣንንም አበረከተችላቸው ለ12 ዓመታትም ከሰማይ ካህናት ጋር አጠኑ ድንግል ማርያም እንዳንተ ውዳሴየንና ቅዳሴየን በፍቅር የሚደግምልኝን እባርከዋለሁ አለቻቸዉ።

ጌታ ደግሞ ገዳማቸውን ዋልድባን ቀድሷታል
ቀድሞም በስደቱ ባርኳት ነበር የጻድቁ ዜና ፈጽሞ ብዙ ነውና ለዛሬ በዚህ ይብቃን
የዋልድባው ኮከብ አቡነ ሳሙኤል ያረፉት ታሕሳስ 12 ቀን በ1395 ሲሆን ዕድሜያቸውም 100 ዓመት ነበር።

የዋልድባው ጻድቅ የአባ ሳሙኤል ኮከብ በረከቱ አይለየን አሜን!!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

21 Dec, 10:09


https://t.me/agent45361719sadorshome


ኑ እየተማርን እየተጨዋወትን ወንበር ላይ ቁጭ ብለን እንለወጥ እንተጋገዝ

👉@SDS12317212729 አውሩኝ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

21 Dec, 08:09


#ሚካኤል_ሆይ የተጨነቀውን የተጨቆነውን ነፃ የምታወጣው መልአክ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን ሠራተኛው ሠርቶ እንዲበላ ውሎ እንዲገባ የምትጠብቀው ሚካኤል ሆይ #ሰላም_ላንተ_ይሁን ።

#ሚካኤል_ሆይ ችግረኛውን ለመርዳት ከልዑል ዘንድ የምትላክ ሚካኤል ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን አዳኝነትህን በማመን የለመነህን ሁሉ በክንፈ ረድኤትህ የምትሰውረው ሚካኤል ሆይ #ሰላም_ላንተ_ይሁን ።

#ሚካኤል_ሆይ በኀዘን በትካዜ ላይ ወድቆ የሚፍገመገመውን የሚንፈራገጠውን ፈጥነህ ደርሰህ ደግፈህ የምታጽናናው ሚካኤል ሆይ አንገትህን ዘንበል ቀለስ አድርገህ በፈጣሪህ ፊት ሰግደህ እኛን ባሮቹን በቸርነቱ ይጎበኘን ዘንድ አማናዊት እጁን ዘርግቶ ይባርከን ዘንድ ለምን አማልድ ።

አቤቱ የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤል አምላክ ሆይ በአርአያህ በአምሣልህ የፈጠርከን ሕዝቦችህን ሁሉ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ሠውረን ለዘላለሙ አሜን ። #መልክአ_ቅዱስ_ሚካኤል

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

21 Dec, 08:07


አዲስ ዝማሬ ዲ\ን ዘማሪ አላዶር ሲሳይ ሚካኤል አስምአኒ ቃለ Diacon/Zemari/Alador sissay
https://youtube.com/watch?v=d-UJM2PEO84&si=F04tPQXcCSzJGiME

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

20 Dec, 17:06


የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰማያዊ ዜማ ከዓመት እስከ ዓመት ያለማቋረጥ የሚዘመርባት ሁለተኛ ጽርሐ አርያም ነች።

ቅዱስ ያሬድ መንፈስ ቅዱስ እንዳመለከተው ሰማያዊ ዜማን ወደ ምድር አወረደ ስም በተግባር ተገለጠ ‹‹ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ። ›› ተብሎ በእግዚአብሔር ቃል የተነገረውና የተመሰከረው ንጹሑ አምልኮቷ በሰማያዊ ዜማ ታጅቧልና።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በየትኛውም ክፍለ ዓለም የማይገኘውን ዜማ ተቀዳጀች በዚህ ዜማ ነገረ እግዚአብሔርን ስትሰብክ ሃይማኖቷን ስትመሰክር ኖረች ወደፊትም ትኖራለች ይህ ልዩ ጸጋዋ ነው ፡፡
©
ሊቁ ቅዱስ ያሬድ የዝማሬ ፣ የፍልስፍና ፤ የስነ ከዋክብት ፤ የሕግ የታሪክ ፣ የመልክዐ ምድርና የቋንቋ ሊቅ የሆነው ዛሬ ዓለም ለደረሰበት የዜማ ፣ የተፈጥሮ ሳይንስና የማኅበራዊ ሕይወት ፍልስፍናም መሠረት ነው ሊያስብል የሚያስችሉ ሰማያዊ ሰነዶችን ትቶልን የሄደ ኢትዮጵያዊ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ነው።

ዛሬ ታኅሣሥ 11 ዓመታዊ በዓለ ንግሱ ነው ዜማው ወደ ቤተክርስቲያን የገባበት የታኅሣሥ 7 ተውላጥ የመታሰቢያ በዓሉ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ባለ ሆኔታ ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ካህናትና ህዝበ ክርስቲያኑ ደምቆ በታየበት ሆኔታ አክብረን ዋልን የዓመት ሰው ይበለን።

በረከቱ ይደርብን🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

19 Dec, 08:08


እንዳያመልጣችሁ ከ24 ሰዓታት ውስጥ እክቲቭ የሆነ 5 ሰዓታትን ብቻ የሚፈልግ ሥራ ነው ኦርቶዶክሳውያን በጋራ መለወጥ ላይ በጣም እንታማለን ምክንያቱም ስለማንተማመን ነው እኔ በጣም ሰነፍ ሆኜ በሦስት ቀን ይኽንን ዶላር የሠራሁት ከጎበዛችሁ ብዙ መሥራት ትችላላችሁ በተለይ ሴቶች እድሉን ተጠቀሙበት ነገ እንዳንቆጭ በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ በዚህ ፕላትፎርም ቀደም ብለዉ የጀመሩ በወር ከ100,000 ብር በላይ ይሠራሉ እኛ እግዚአብሔርን አመስግነን በወር 100 ዶላር በጣም ትንሹ ማለት ነው ብንሠራ በቂያችን ነው ሥራ ያለንም የሌለንም የማንጎዳበት ነው ስለዚህ ኑ አብረን እንሥራ

👉@SDS12317212729 አውሩኝ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

07 Dec, 14:20


https://youtube.com/channel/UCty44f8sgNw0YhHckK_bX4Q?si=Jd0lVljigX1UiHad

Subscribe

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Dec, 11:26


//የንግስ በዓል ጥሪ// ሐመረ ኖኅ ሚዲያ
https://youtube.com/watch?v=y1u_pX2lfAo&si=OIJjW4xgPyBK2KvK

የኔ አባት የምንናፍቀዉ ክብረ በዓሉ ደረሰ
ማስታወቂያዉን እያየን ሼር ላይክ በማድረግ
እስከዛዉ ደግሞ ሐመረ ኖኅ ሚድያን እየተወዳጃችሁ ሰብስክራይብ እያደረጋችሁ ቆዩ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Dec, 06:48


#ትዕቢት እና #ውዳሴ_ከንቱ

በዕለተ ስቅለት የስቅለት ምክንያት የሆነ ሳጥናኤልን እና በቀራንዮ አደባባይ በመስቀል ላይ የነበረዉን ፈያታዊ ዘፀጋም ዳክርስን ባሰብኩ ጊዜ........

ውኃ በመጽሐፍ ላይ በነጠበ ጊዜ ቀለሙ እንደሚጠፋ መልካም ገድልም በውዳሴ ከንቱ ትጠፋለች።

የፋሲካ በግ በሥውር ይበላል
መልካም ሥነ ምግባራትም በሥውር ይጠበቃሉ።

በአፍኣ የጎሰቆለች በባሕርይዋ ንጽሕት ትኾናለች የተሠወረች መልካም ሥራም በእግዚአብሔር ፊት ትደምቃለች እንዲህም ስለሆነ ሰውነትህን ለውዳሴ ከንቱ አሳልፈህ አትስጥ።

የትዕቢት ብዛት የነፍስ ቁስል ነው
ኃፍረትንም የተመላ ነው።

የትዕቢተኛ ሰው ነፍሱ ከፍ ከፍ ትላለች
ነገር ግን ፈጥና ወደ ጥልቁ ትወድቃለች

ድንጋይ ከተራራ ላይ በተፈነቀለ ጊዜ ፈጥኖ እንዲወድቅ እንዲቀጠቀጥ ትዕቢተኛ ሰውም እንዲሁ ፈጥኖ ይወድቃል ከእግዚአብሔርም ይለያል።

ለትዕቢተኛ ሰው እግዚአብሔር የፈጠራቸው ፍጥረታት ሁሉ ኃይል የሌላቸው ይመስለዋል

በሸረሪት ድር የሚጫን ወዲያውን ይወድቃል
በራሱ ኃይል የሚመካም እንዲሁ ይጠፋል

የፍሬው ብዛት ዛፉን ያዘነብለዋል (ዝቅ ዝቅ ያደርገዋል የበጎነት ፍሬ ብዛትም ሰውን ትሑት ያደርገዋል

የነቀዘ የስንዴ ቅንጣት ለዘር አይጠቅምም አይሆንም የትዕቢተኛ ሰው በጎ ሥራም መቼም መች እግዚአብሔርን ደስ አያሰኘውም

የአትክልት ቦታን የሚንከባከብ ሰው ፍሬን የተሞላችውን ተክል ለይቶ ከፍ ከፍ ያደርጋታል የፈሪሃ እግዚአብሔር ፍሬም በጎነት የተመላችውን ሰውነት ታጸናታለች

ሌሊት የምትሐት ሕልሞችን እንዳታይ ልቡናህን ለትዕቢት አሳልፈህ አትስጥ።

#አባ_ወግሪስ_ገዳማዊ

ከትዕቢት መንፈስ እና ውዳሴ ከንቱ ፍቅር ቸር መድኀኔ ዐለም ይጠብቀን።

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Dec, 05:33


#መድኀኔ_ዐለም

የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ስቅለት ስናስብ የምናስበው በእራሱ ላይ የደፋውን የእሾህ አክሊል ነው ታስሮ የተጎተተበትን ገመድ ነው የጠጣውን ሆምጣጤ ነው የተወጋበትን ጦር ነው።

እነዚህ ሁሉ እኛን ስለመውደዱ የተቀበላቸው ስለእኛ ፍቅር የተከፈሉ ዋጋዎች ናቸው ይህን ቅዱስ ኤፍሬም "እግዚአብሔር መፍቀሬ ሰብዕ ዘዚአነ ሞተ ነስአ ወእንቲአሁ ሕይወተ ወሀበነ" ሰውን የሚወድ እግዚአብሔር የእርሱን ሕይወት ለኛ ሰጥቶ የእኛን ኅማም ለራሱ ወሰደ ብሎ ነግሮናል።

ጌታን እኛን ለማዳን የከፈለው ዋጋ እና እኛ ደግሞ በአንጻሩ ላለመዳን የምናደርገው ጥረት ሁለቱ ሁልጊዜ የሚያስገርሙ ናቸዉ!

ላለመዳን ያደረግነውን ጥረት የከፈልነውን ዋጋ ለመዳን ከፍለነው ቢሆን ሁላችንም መላእክት ነበርን!

ለኃጢአት ከምንደክመው ሩቡን ለጽድቅ ለመዳን ብንደክም ማን እንደኛ እድለኛ ነበር!?

እኛ ለበደል ከምንደክመው በላይ የእግዚአብሔር ምሕረት እጆቹ የተዘረጉ ናቸው።

በዕለተ ዐርብ ከተከናወኑ ታሪኮች አንዱን እናስታውስ

#መድኀኔ_ዐለም ዕርቃኑን በእንጨት ላይ ተሰቅሎ ሳለ ከአይሁድ ጋር ጌታን በመስቀል ያልተባበረ በሰዓቱ ያልነበረ ለንጊኖስ የተባለ አንድ ዐይና ሰው ጌታ ከተሰቀለ በኋላ መጥቶ ተራውን በዘገር ጦር ጎኑን ሲወጋው ደሙ ተፈናጥሮ ዐይኑን አብሮቶለታል።

ጌታ ሰውን ወዳጅ ተብሎ የሚነገርለት እንደሁ አይደለም ያውም ለገዳዮቹ የሚያደርገውን እንክብካቤ ለወዳጆቹ አላደረገውም

ዛሬም ብዙ ለንጊኖሶች አለን በኃጢአት ጦር በነውር ጦር በሐሰት ጦር በቅናት በምቀኝነት ጦር በዝሙት ጦር ቀን በቀን የጌታን ጎን የምንወጋ ጥቂቶችም አይደለንም!

የመኖሯችን ምሥጢር ጥሩ ሰዎች ስለሆንን አይደለም እግዚአብሔር ጠላቶቹን ወዳድ ስለሆነ ነው ለሁላችንም እንደ ለንጊኖስ የመዳኛ መንገድ እየፈለገልን ነው።

ለንጊኖስ ወዲያውኑ ለካ በጦር የወጋሁት ወዳጄን ነው ብሎ ተመልሷል እንዲያውም ክሶታል ደሙን ያፈሰሰውን ያህል ደሙን አፍሶለታል።

የለንጊኖስን ዐይን ያበራ #መድኀኔ_ዐለም የእኛንም ዐይነ ልቦናችንን ያብራልን!


#እንኳን_አደረሳችሁ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Dec, 06:43


#ጻድቅ_አባታችን_ሀብተ_ማርያም

...« ቅድስት ዮስቴና ሆይ ከሕጋዊ ባልሽ ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ እርሱም ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ፣ ሰው ሁሉ የሚማፀነው ፣ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም የሚነገርለት ፣ በነፍስም በሥጋም የሚያማልድ ፣ እንደ መልአክትም ክንፈ ጸጋ የሚሰጠው በምድር ሆኖ መንበረ ጸባኦትን የሚያይ ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ » ተብሎ ትንቢት የተነገረላቸው የአባታችን የጻድቁ #የአቡነ_ሀብተ_ማርያም ልደት ግንቦት 26 ቀን በታላቅ ድምቀት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ታከብራለች ።

« በጸሎትህ አምኖ በጎ ሥራ ለሚሠራ ሁሉ ስምህን የጠራውን ዝክርህን የዘከረውን ሁሉ የሀብተ ማርያም አምላክ ሆይ ከጠላት እጅ አድነኝ ያለኝን በኅሊና ያሰበውን በልቡናው የወሰነውን እፈጽምለታለሁ ። » ብሎ ቃልኪዳን የተገባልህ እኛን ደካማ ልጆችህን በምልጃህ በቃል ኪዳንህ አስበን።

#እንኳን_አደረሳችሁ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

03 Dec, 05:34


#ምድራዊ_ሱራፊ_አቡነ_ተክለ_ሃይማኖት_ጻድቅ

ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ሆነው ያጠኑ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከመንደር ከሰፈር ወጥተው በዛሬዋ ዕለት ወደ ሰማይ በመውጣት በመንበረ ጸባዖት በሰማያዊ ማዕጠንት ከካህናተ ሰማይ ጋር አብረው ያጠኑ ምድራዊ ሱራፌል ናቸዉ።

#እኛ_የኦርቶዶክስ_ተዋሕዶ_ልጆች_በምልጃቸው_እንታመናለን !!!

#ጸሎታቸዉ_ትራዳን_ቃል_ኪዳናቸው_አትለየን!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

03 Dec, 05:30


#ለሰው_ልጅ_ምሕረትን_የሚለምኑ_አማላጆች!

#ኅዳር_24_ቀን በእግዚአብሔር ዙፋን ዙሪያ የሚኖሩ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ የሚዘከሩበት ዓመታዊ በዓላቸው ሲሆን በተጨማሪም በዚህ ዕለት ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከካህናተ ሰማይ ጋር በመንበረ ጸባዖት በሰማያዊ ማዕጠንት ያጠኑበት ዕለት ነው፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በስማቸው ቤተ ክርስቲያን አንጻላቸው ታቦት ተቀርጾላቸው ዓመታዊ በዓላቸውን በታላቅ ድምቀት እንዲከበር ታደርጋለች።

#ካህናተ_ሰማይ ስማቸውም ‹‹ ሱራፌል ›› ይባላል ቃሉ የዕብራይስጥ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ እሳታውያን ›› ማለት ነው ነገዳቸው ነገደ ሚካኤል ነው።

#ካህናተ_ሰማይ ሥጋ የሌላቸው ረቂቃን የእውነት ካህናት የሆኑ ከቅዱሳን ሁሉ በላይ የሆኑና ከሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከፍ ከፍ ያሉ ናቸው እነርሱም ለእግዚአብሔር ቀራቢዎች በመሆን ለሰው ወገን የሚማልዱ ከእጃቸው ውሰጥ ካለ ማዕጠንት ጋር እንደ ዕጣን የቅዱሳንን ጸሎት የሚያቀርቡ የሚያሳርጉ ናቸው።

#ሰማያውያን_ካህናት በግርማ መጎናጸፊያ ይሸፈናሉ ያለማቋረጥ መንበረ ፀባዖትን ያጥናሉ እሳተ መለኮቱ እንዳያቃጥላቸው ተሸፋፍነው የማዕጠንቱን ሥርዓት ያከናውናሉ ተፈጥሯቸውም ስድስት ስድስት ክንፍ ያላቸው ዐይንን የተመሉ ናቸው።

#ካህናተ_ሰማይ እሳታዊ የወርቅ ማዕጠንት የሚይዙ የብርሃን ዘውድ የተቀዳጁ ኅብሩ በረዶ የመሰለ የብርሃን ካባ ላንቃ የሚለብሱ የጻድቃንን ጸሎት ፣ የሰማዕታትን ገድል ፣ የበጎ ሰዎችን ምግባር ትሩፋት የሚያሳርጉ ናቸው።

#ካህናተ_ሰማይ የአማልክት አምላክ እግዚአብሔር ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ነው የነበረ የሚኖር በመዓልትና በሌሊት የሚኖር ነውና ያለ ዕረፍት ሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ አክሊላቸውን በዙፋኑ ፊት አውርደው ለዘላለሙ ሕያው ለሚሆን በዙፋን ላይ ለተቀመጠው ለእሱ ስገዱለት እያሉ ያመሰግኑታል።

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ እንዲህ ሲል በድጓው መስክሯል ‹‹ ለሰው ልጅ ምሕረትን የሚለምኑ አማላጆች ምርጦች የአብ ወዳጆቹ አብን በአንድነት ያመሰግኑታል ሳያቋርጡ ፈጽመው ያመሰግናሉ ፣ ክብራቸው ከመላእክት ይበልጣል ! ግሩምና ድንቅ ዕፁብ ሥራ ለካህናት አሳያቸው ፡፡ ›› በማለት ዘምሯል።

ሰለዚህም ከፈጣሪያችን ከፈጣሪያችው ያማልዱንና ያስታርቁንም ዘንድ የበዓላቸውን መታሰቢያ እንድናደርግ፤ የጸጋ ስግደትና ምስጋና እንደሚገባቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትን ሰርታልናለች።

#የቅዱሳን_መላእክት_ሱራፌል_ካህናተ_ሰማይ_በረከታቸዉ_ምልጃ_ጸሎታቸዉ_አይለየን!

#እንኳን_አደረሳችሁ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

30 Nov, 06:05


🛑የእመቤታችን መዝሙራት🛑 የግእዝ መዝሙራት ስብስብ || St. Mary Mezmurs Collection I @lis...
https://youtube.com/watch?v=fsasWALzU9I&si=Ymv8Ir6Yg9lJrRLV

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

30 Nov, 04:31


#ጽዮን_የምድር_ሁሉ_ደስታ_ናት !!!

እስራኤልላውያን ከግብፅ ከባርነት ከወጡ በኋላ ጸልየው እንዲድኑባት ሰውተው እንዲከብሩባት ታቦተ ጽዮንን እግዚአብሔር አምላክ ሰጣቸው በታቦተ ጽዮን እየተማፀኑ አርባ ዘመን ደመና እየጋረደ መና እያወረደ ዐለት እየሰነጠቀ ውኃ ከጭንጫ እያፈለቀ በሰላም ተንከባክቦ መግቦ ምድረ ርስት አግብቷቸዋል። #ይህች_ታቦተ_ጽዮን

ቅጽረ ኢያሪኮን ያፈረሰች።
የዮርዳኖስን ባሕርን የከፈለች።
በድፍረት ሊነካት የሞከረ ኦዛንን የቀሠፈች።
ዳጎን የተባለ የፍልስጤማውያንን ጣዖት ቆራርጣ ያጠፋች።
በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀምጣ ቤቱን በበረከት የመላች።
ከብዙ ዘመን በኋላ ወደ ሀገሯ ስትመለስ ነቢዩ ዳዊት በደስታ የዘመረላት።
ንጉሥ ሰሎሞን በወርቅ የተጌጠ ቤተ መቅደስ ሠርቶ በክብር ያኖራት።
በደብተራ ኦሪት በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ተቀምጣ ያለች ናት።

የእግዚአብሔር የክብሩ መገለጫ ታቦት የሆነችው ይህች በንጽሕና በቅድስና የተጌጠችው የእግዚአብሔር ወልድ እናት የሆነችው የአማናዊት ታቦት የቅድስት ድንግል ማርያም ምሳሌ ናት፡፡

የአምላክ ማደሪያ የሆነችው ታቦተ ጽዮን ወደ ፍልስጥኤም ሀገር ሔዳ ዳጎንን ሰባብራ እንዳጠፋች ሁሉ አማናዊት የጌታ ታቦት ቅድስት ድንግል ማርያምም ጌታን ይዛ ወደ ግብጽ በተሰደደች ጊዜ የግብጽ ጣዖታትን ሁሉ እየተሰባበሩ እንደወዳደቁና እንደደቀቁ በኢትዮጵያ ሀገራችን በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን ጠላት ካሴረባት ሸፍጥ ሁሉ እግዚአብሔር አምላካችን ይታደጋት፡፡

#እንኳን_አደረሳችሁ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Nov, 05:43


በዚች ቀን ታላቅና ክቡር የሆነ የዓለሙ ሁሉ መምህር የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት የዮሐንስ አፈወርቅ ሥጋው የፈለሰበት ነው።

ይህም እንዲህ ነው መበለቲቱን ቦታዋን በግፍ ነጥቃታለችና እርሱም እንድትመልስላት ቢያዛት ስለ አልሰማችው ስለ መበለቲቱ ቦታ ቅዱስ ዮሐንስ ንግሥት አውዶክስያን በአወገዛት ጊዜ በእርሱ ላይ ተቆጣች ሰይጣንም በልቧ አደረና ስለ ክፉ ሥራቸውና ስለ በደላቸው አውግዞ የለያቸውን ኤጲስቆጶሳት በእርሱ ላይ ሰበሰበች።

እነርሱም ስለ መሰደዱ ከእርሷ ጋር ተስማምተው አድራኮስ ወደምትባል ደሴት አጋዘችው በዚያም ጥቂት ዓመታት ኑሮ ወደ መንበረ ሲመቱ ተመለሰ። ከዚህም በኋላ ዳግመኛ መናፍቃን የሆኑ ኤጲስቆጶሳትን ሰበሰበችና ወደ አርማንያ አጋዙት ከዚያም በረሀ ወደ ሆነ ሩቅ አገር ሰደዱትና በዚያ አረፈ።

የአርቃዴዎስም ልጅ ታናሹ ቴዎዶስዮስ በነገሠ ጊዜ መልክተኞችን ልኮ የቅዱስ ዮሐንስን ሥጋ ብዙ በመዘመርና በማመስገን በታላቅ ክብር ወደ ቊስጥንጥንያ አፍልሶ አስመጣው ይህም ከዕረፍቱ በኋላ በሠላሳ አምስት ዓመት ነው። በሌላ በቅብጢ መጽሐፍ በግንቦት ወር ሃያ ሁለት ቀን እንደ ደረሰ ይናገራል በሮማውያን መጽሐፍ ግን በየካቲት ወር ሃያ ሁለት ቀን ተባለ የዕንቊ ፈርጾች ባሉት የዕብነ በረድ ሣጥን ውስጥ አድርገው ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት ከሥጋውም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።

የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በረከቱ ይደርብን!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Nov, 05:29


"ዘኢያደሉ ለገጽ" የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ አዲስ ዝማሬ በፍኖተ አፈወርቅ
https://youtube.com/watch?v=MBKSklYDrmk&si=E9cX8PV9vOw1vITY

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

25 Nov, 11:37


ጸሎት

#ጸሎት በሕይወታችን ውስጥ ደንብና መደበኛ ልምምድ መሆን አለበት ፤ ይህም በጽድቅና በአክብሮታዊ አቋቋም እንዲሁም ፍጹም በሆነ ትኩረት ሊከናወን ያስፈልጋል። በጸሎት ጊዜ ከእግዚአብሔር ጋር ስንነጋገር ለእርሱ የሚገባውን ተገቢ ክብር መስጠት አለብን የጸሎትን ታላቅ ጥቅም ማወቅ አለብን። በግላችንም የተለየ ምላሽ መኖራቸውን መገንዘብ አለብን። ጸሎት ከእግዚአብሔር ጋር በእውነት የመነጋገር ያህል የሆነለት ሰው ምድራዊ መላአክ ሆኖ ተለውጧል ማለት ነው።

እግዚአብሔር አምላክ ከእርሱ ጋር ስንነጋገር የተዋቡ ቃላትን እንድንጠቀም አይጠይቀንም። ይሁን እንጂ የምንነጋገራቸው ቃላት ከተዋበ ነፍሳችም ተፈንጥቀው መውጣት አለባቸው ጸሎት በተለመደበት ሰዓት ሲቀርብ ሽምጋዮችን፤ስርዐቶችን ወይም ቀጠሮዎችን አይሻም። የእግዚአብሔር ደጆች ዘወትር ክፍት ስለሆኑ እርሱ እኛን ይጠብቀናል እራሳችንን ከእግዚአብሔር የምናገል ወይም የምናርቅ ከሆንን ሙሉ በሙሉ በራሳችን ሀሳብ መደገፍ ይጀምራል ማለት ነው። እርሱ ዘወትር ቅርብ ነው። በተለየ ሁኔታ አንደበተ እርቱ መሆን አያስፈልገንም። እኛ የተፈለገውን ያህል ድምጻችንን ዝግ አድርገን ብንናገር እንኳን እርሱ ይሰማናል። በጸሎት ጥበብ ውስጥ የተራዘመን መመሪያዎችን ማስቅመጥ አስፈላጊ አይደለም። ለመጸለይ መፈለጋችን በራሱ በቂ ነው።

በቂው ነገር የጸሎት ዘዴ ነው እኛ መጸለይ ያለብንን ከልባችን ሆነን መንፈዊዊ ዕድገት የሚሻ ጸጸት ውስጥ ሆነን ሌሎች ሰዎችን ይቅር ለማለት የእርሱን ይቅርታ መጠየቅ እንዲሁም የእውነት ትሁት ሰው መሆን ነው። እግዚአብሔር  እንደሚፈልገን ሆነን የምንጸልይ ከሆነ። ጸሎታችን ባለ መታከት የምናቀርብ ከሆነ፤ በጸሎታችን ውስጥ ለእኛም ሆነ ለሌሎች ነፍሳት ጥቅም ጉዳይ ላይ የምናተኩር ከሆንን ጸሎታችን አድማጭ ተቀባይ ያገኛል።

በምንጸልይበት ጊዜ ጸሎታችን መጋነን የለበትም ፤ ጥረቶቻችን ሙሉ ለሙሉ በመቀበል ሐሳብ ላይ ብቻ ማተኮር የለባቸውም። ዋናው አላማችንና አስፈላጊ ነገር ነፍሳችንን የተሻለ ማድረግ ነው ፣ ይህም ሊሆን የሚችለው በጸሎት አማካኝነት ነው። ይህን ጉዳይ አላማው አድርጎ የሚጸልይ ሰው ከዓለማዊ ነገሮች ኃይል ይበልጥ ብርቱ ይሆናል ከእርሱ ጋር በላይም ከፍ ብሎ ሊከናወንለት ይችላል።

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

17 Nov, 03:29


#አርባዕቱ_እንስሳ

አርባዕቱ እንስሳ ስለምንላቸው ቅዱሳን መላእክት በብሉይ ኪዳንም በሐዲስ ኪዳን ተጽፎ እናገኛለን

ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም

ሰዓሉ ለነ አርባዕቱ እንስሳ ሱራፌል ወኪሩቤል አጠንተ መንበሩ ለልዑል

የልዑል እግዚአብሔር መንበርን የምታጥኑ በገፀ አንበሳ በገፀ ንስር በገፀ ላኅም በገፀ ሰብዕ የተመሰላችሁ ሱራፌል እና ኪሩቤል ሆይ ለምኑልን አማልዱን እያለ የሥራ ድርሻቸውን በመግለጽ ጽፏል

ቅዱስ ያሬድም ሶበሰ ይወርዱ መላእክት አልቦሙ ድምጽ ወአልቦ ሀሰር ለምክያዳቲሆሙ ይቀልል ሩጸቶሙ እምነፋሳት

መላእክት ለተልዕኮ በሚወጡ በሚወርዱበት ጊዜ ድምጻቸው አይሰማም በዚህ ወጡ በዚህ ገቡ አይባሉም ፍጥነታቸውም ከነፋስ ይበልጣል እያለ አገልግሎታቸውን ኃያልነታቸውን ፍጥነታቸው ይገልጻል

መጽሐፍ ቅዱስን ስናገላብጥ ለእያንዳንዳቸው ስድስት ስድስት ክንፍ እንዳላቸው ይናገራል ለሚካኤልም ለገብርኤልም ለሌሎች መላእክትም ስድስት ክንፍ አላቸው አይልም ከማሕበረ መላእክት በተለየ መልኩ ለእነሱ ግን ስድስት ስድስት ክንፍ እንዳላቸው ይናገራል ሊቃውንቱም በቂ የሆነ ትርጉም አስቀምጠዋል

ከማሕበረ መላእክት መካከል ለእግዚአብሔር ቅርብ የሆኑ ዙፋኑን የሚሸከሙ መንበሩን የሚያጥኑ እግዚአብሔር ዘባናቸውን ዙፋን አድርጎ የሚገለጥባቸው እንደሆኑ ሊቃውንቱ በየድርሰታቸው ጽፈዋል በረከታቸው ይደርብን ቃል ኪዳናቸው ይጠብቀን!

ኅዳር 8 የአርባዕቱ እንስሳ ዓመታዊ በዓላቸው ነው በረከታቸው ይደርብን

እንኳን አደረሳች

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

16 Nov, 06:12


#ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሊቀ_ሰማዕት

ኅዳር ሰባት በዚህች ቀን የልዳ ሀገር የሆነ የሰማዕታት አለቃ የታላቁ መስተጋድል የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የከበረችበት ነው ዳግመኛም ጌታችን በውስጧ ላደረገው ድንቅ ተአምር መታሰቢያ ሆነ።

ይህም እንዲህ ነው በውስጧ ድንቆች ተአምራት እንደሚሠሩ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስ በሰማ ጊዜ ሊያፈርሳት አሰበ ስሙ አውህዮስ የሚባለውንም መኰንን ከብዙ ሠራዊት ጋር ላከው ያም መኰንን በደረሰ ጊዜ የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል ወዳለበት አዳራሽ በትዕቢት ሆኖ ገባ በሥዕሉም ፊት በብርጭቆ መቅረዝ መብራት ነበረ በቤተ ክርስቲያኒቱና በቅዱስ ጊዮርጊስ ላይ እየዘበተ በእጁ በያዘው በትር የመብራቱን መቅረዝ መትቶ ሰበረው የመቅረዙም ስባሪ ወደ ከሀዱው ራስ ደርሶ መታው ራሱንም ታመመ ፍርሃትና እንቅጥቅጥም መጣበት ወድቆም ተዘረረ ባልንጀሮቹም ወደ አገሩ ሊወስዱት ተሸከሙት በክፉ አሟሟትም ተጐሳቊሎ ሞተ ወስደውም ከባሕር ጣሉት ወገኖቹም ወደ ሀገራቸው አፍረው ተመለሱ።

ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ ተቆጣ በልዳ ሀገር ያለች የቅዱስ ጊዮርጊስን ቤተ ክርስቲያን ያፈርሳት ዘንድ ራሱ ተነሥቶ ሄደ በዚያንም ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መታው ሰባት ዓመት ያህልም ዐይኖቹ ታውረው አእምሮውንም አጥቶ ቁራሽ እንጀራም እየለመነ ኑሮ ሞተ።

ክብር ይግባውና ጌታችንም የቤተ መንግሥቱን ሰዎች አስነሣበት እርሱን አስወግደው ጻድቅ ሰው ቆስጠንጢኖስን በእግዚአብሔር ፈቃድ አነገሡት እርሱም በአዋጅ የጣዖታትን ቤቶች ዘግቶ አብያተ ክርስቲያናትን ከፈተ ለክርስቲያን ወገኖችም በሁሉ ዓለም ተድላ ደስታ ሆነ።


#የቅዱስ_ጊዮርጊስ_ጸሎቱ_ትራዳን_በረከቱም_ይደርብን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

15 Nov, 05:27


#ሱላማጢስ_ከስደት_ተመልሳለችች_የኛስ_መመለሳችን_መቼ_ይሆን ?

#ኅዳር_ስድስት ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አዝላ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ሦስት ዓመት ከመንፈቅ በስደት ከኖሩ በኋላ ቅዱስ ገብርኤል ለዮሴፍ እንዲህ አለው

« ሕፃኑን የሚሹት ሄሮድስና ሠራዊቱ ሞተዋልና እናቱንና ሕፃኑን ይዘህ ወደ ሀገርህ ተመለስ » ማቴ፡ 2 ፥ 19 ባለው ጊዜ አረጋዊ ዮሴፍ እናትና ልጁን ይዞ ሰሎሜን አስከትሎ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ከስደት ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሱ ደብረ ቁስቋም በተባለ ቦታ ያረፉበት ተራራ ነው።

ዐምስት ሺ ዐምስት መቶ ዘመን ሙሉ ሰላም ላጣ ለአዳም ሰላም የሆነች
« ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር » ተብሎ በክብር እንዲመሰገን ምክንያት የሆነች የሰላም አናት የሰላም እመቤት ድንግል ማርያም #ሱላማጢስ_ከስደት_ተመልሳለች ።

እኛስ መቼ ይሆን ዛሬ በኀጢአት ስደት ያለን ብዙዎች ነን የሠራነው ኀጢአት ከእግዚአብሔር ፊት ከቤተ ክርስቲያን ደጅ ያሳደደን ብዙዎች ነን በትዕቢት ልብ ተይዘን ትላንት ካስቀደስንባት ፣ ከቆረብንባት ከቀደስንባት ከተማርንባት ካስተማርንባት ደጅ የተሰደድን #መመለሳችን_መቼ_ይሆን ?

መቼ ይሆን ? ከሥጋ ወደሙ የተሰደድን ከልጅነት ጊዜያችን በኋላ ፣ከትዳራችን በኋላ ፣ከአገልግሎታችን በኋላ ሥጋ ወደሙን መቀበል ያቆምን ከሕይወት ምግብ የተሰደድን ሥጋችን እየደለበ ነፍሳችን የቀጨጨችብን #መመለሳችን_መቼ ይሆን ?

ከአገልግሎት የተሰደድን ትላንት እንዘምር ፣ እንማር እናስተባብር የነበርን አገልጋዮች ዛሬ የት ነን ? መመለሳችን መቼ ይሆን ?

#ወዳጄ_በቤተ_ክርስቲያን_አለሁ_እንጂ_ነበርኩ_አያድንምና ያለነው የነበርንበት ቦታ ካልሆነ ወደ ነበርንበት እንመለስ በደልን እንጂ በደለኛን ወደ ማይጠላ አምላክ እንመለስ የት ናችሁ ስንባል ከምናፍርበት ቦታ እንዳንገኝ ወደ ደገኛይቱ ቤት ወደ ቤተ ክርስቲያን እንመለስ።

#እንኳን_አደረሳችሁ!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

13 Nov, 06:00


ጌታችንም በተስቀለ ጊዜ #ቅዱስ_ዮሐንስን እነሆት እናትህ ብሎ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እመቤታችንን በአደራነት ሰጥቶታል እሷንም እነሆ ልጅሽ ብሎ አስረክቧታል ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስም በአደራ የተቀበላትን የአምላክን እናት እመቤታችንን ለ 15 ዓመታት ያህል እያገለገለ እያመሰገነ የኖረ ታላቅ ሐዋርያ ነው ።

እመቤታችንም ከዚህ ዓለም ስታርፍ በክብር ገንዞ የቀበረ ሐዋርያ ነው አይሁድ አላስቀብርም ብለው ባዐመፁ ጊዜም መልአኩ የእመቤታችንን ቅዱስ ሥጋ ነጥቆ በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ባኖራትም ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ እየተነጠቀ በየጊዜው ሥጋዋን እያጠነ ይመለስ ነበር ።

ፍቁረ እግዚእ የተባልክ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ሆይ

ስላገለገልካት እናትህ እናታችን ብለህ አማላጅነትህ አይለየን

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

12 Nov, 07:22


በሊቀ ካህኑ በዘካርያስ እጅ በእግዚአብሔር ፊት የቀረበች ንጹህ መስዋዕት የሐና እና የኢያቄም መባ አማናዊት ቤተ መቅደስ ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዕለት በሥዕል ሲገለጽ

ቅዱሳት ሥዕላት ከሥዕለ አድኅኖነታቸው ባሻገር የአንድን ቅዱስ ወይም ቅድስት የሕይወት ታሪክ የሚያሳዩ መስታውቶች ናቸው

ሥዕልን ታሪክ አዋቂ የተማረ ይሳል እንጂ በልምድ እንዳይሆን የሚባለው ለዚያ ነው

የመጀመሪያው ሰዓሊ ቅዱስ ሉቃስ ነው

ቅዱስ ሉቃስ እመቤታችን በአካል ከሚያውቋት ቅዱሳን መካከል አንዱ ነው

ይህ ቅዱስ የሳላት የእመቤታችን ሥዕል ተናጋሪዋ ሥዕል በመባል ትታወቃለች

ሥዕሉን ስታዩት ሁለት አይነት ሥዕል ታገኛላችሁ አንደኛው እመቤታችንን ብቻ የሚያሳይ ሲሆን አረጋዊው ዮሴፍ ያያት በነበረው መልክ የተሣለች ናት

ሁለተኛው በሉቃስ እጅ ያለው ሥዕል የሉቃስን ታሪክ ያሳያል የተቆረጠ እጅ ያለበት ነው ይህም ቅዱስ ሉቃስ ተናጋሪዋን ስዕል በመሣሉ ጠላት እጁን እንዲቆረጥ አድርጎታል ይህን ታሪክ ይገልጻል

#ልመናዋ_ክብሯ_ፍቅሯ_በረከትዋ_ይደርብን

እንኳን አደረሳችሁ!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 12:46


Channel photo updated

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 10:12


.                     ና  ሁ ፡ ተ  ፈ  ጸ  መ ፡ ማ  ኅ  ሌ  ተ ፡ ጽ  ጌ
           ༺◉❖═───◉●◉🌹🌹🌹◉●◉────═❖◉༻
በዐይናችን ሥዕለ ማርያምን እያየን በጆሯችን ዜማውን እያዳመጥን በአፍንጫችን የሚታጠነውን ዕጣን እያሸተትን በአንደበታችን እያዜምን ፤ በእግሮቻችን እያሸበሸብን በእጆቻችን ከበሮ እየመታንና እያጨበጨብን በመላው ሕዋሳታችን ለእመቤታችን ያለንን ልባዊ ፍቅር የምንገልጥበት ወቅት እነሆ #ማኅሌተ_ጽጌ_ተፈጸመ።

ሊቃውንቱ አጥንታቸው ከሥጋቸው ተለይቶ የሚረግፍ እስኪመስል ድረስ ላባቸው እየተንጠፈጠፈ ያሸበሽባሉ እመቤታችንም በመሐረቧ እንደምትጠርግላቸው በማሰብ በመንፈሳዊ ወኔ ፍቅሯ እያቃጠላቸው ከዕንባ ጋራ ይቆማሉ ምዕመናን ነጫጭ ልብስ ለብሰው በዕልልታና በጭብጨባ ምስጋናውን እየተጋሩ የሚያድሩበት #ማኅሌተ_ጽጌ_ተፈጸመ ።

እመቤታችን የፍጥረት ባለቤት የሆነውን ልጇን አዝላ በምትሰደድበት ጊዜ ፍጥረት ሁሉ አብሮ ተሰዷል ፣ ከሰማያውያን ወገን ቅዱስ ሚካኤል ፣ ቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ኡራኤል ከነሠራዊታቸው ከሰው ልጆች ዮሴፍና ሰሎሜ ከእንስሳት ወገን አህያ ፣አብረው ተሰደዋል እያልን የምናሸበሽብበት #እነሆ_ማኅሌተ_ጽጌ_ተፈጸመ ።

ያዘልሽው ጌታ የእኛም ፈጣሪ ነው ሲሉ ነው ቅዱስ ሚካኤል መልአከ ዐቃቢ ሆኖ ፤ ቅዱስ ገብርኤል መልአከ ብሥራቷ ሆኖ ቅዱስ ኡራኤል መንገድ መሪ ሆኖ ፤ ዮሴፍና ሰሎሜ የሚደርስባትን መከራ ሁሉ አብረው እየተጋፈጡ በቅርብ ሆነው እያረጋጓት አህያዋ የእነርሱን ዱካ እየተከተለች ስንቃቸውን ይዛ አብረው ተሰደዋል ብለን የምናስበት #እነሆ_ማኅሌተ_ጽጌ_ተፈጸመ ።

#ደግሞ_ለዓመቱ_እድሜና_ጤና_ሰቶን_በቤቱም_አጽንቶን    #አንቺ_ሱላማጢስ_ሆይ_ተመለሽ_እናይሽ_ዘንድ_ተመለሽ
#እንል_ዘንድ_ያድርሰን

#እግዚአብሔር_በፈቀደ_በወረባቱ_ለነበረን_ቆይታ_እግዚአብሔርን_እያመሰገን_ከነጉድለታችን_አብራችሁን_ስላላችሁ_እናመሰግናለን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 10:07


አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ pinned «የ፳፻፲፮ ዐ.ም የጽጌ ስድስተኛ ሳምንት ምንባባት 🌹🌹🌹🌹ተፈጸመ ማኅሌተ ጽጌ 🌹🌹🌹🌹 🌼የገባሬ ሰናይ (የ አንደኛዉ) ዲያቆን🌼 🌹🌹🌹🌹🌹ቆላ፡1፥1-12🌹🌹🌹🌹🌹 ¹ በእግዚአብሔር ፈቃድ የኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያ የሆነ ጳውሎስ ጢሞቴዎስም ወንድሙ፥ ² በቈላስይስ ለሚኖሩ ቅዱሳንና በክርስቶስ ለታመኑ ወንድሞች፤ ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ይሁን። ³-⁵ ስለ እናንተ ስንጸልይ፥…»

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 10:07


አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ pinned «🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ምስባክ ዘሳድሳይ ሳምንት ወበዓለ ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ፣ ወኢዮብ ጻድቅ፣ ወአቤል" #ተፈጸመ_ማኅሌተ_ጽጌ" 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ምንባባት፦ ቆላ፡ ፩÷፩-፲፪ ያዕ፡ ፩÷፩-፲፫ ግብ:ሐዋ ፲፫÷፮-፲፮ ማቴ ፮÷፳፭-ፍ:ም ምስባክ፦ ወይከዉን ከመ ዕፅ እንተ ትሁብ ኀበ ሙኀዘ ማይ፣ እንተ ትሁብ ፍሬሃ በበጊዜሃ፣ ወቆጽላኒ ኢይትነገፍ። ትርጉም፦ እርሱም…»

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 10:03


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የስድስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 10:02


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የስድስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 10:02


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የስድስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 10:00


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የስድስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 09:59


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የስድስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 09:58


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የስድስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 09:57


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የስድስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Nov, 09:52


#ቅዱስ_ማርቆስ_ሐዋርያ

በዚህች በከበረች ጥቅምት ፴ ቀን በዓለ ልደቱ ነው።

ማርቆስ ማለት ንህብ ማለት ነው ንህብ ሁሉን እንዲቀስም እሱም ቀድሞ ከጌታ ኃላ ከሐዋርያት ተምሯልና አንድም ልዑክ ማለት ነው ለስብከተ ወንጌል ይፋጠናልና አንድም አንበሳ ማለት ነው አንበሳ ለላም ጌታው ነው ይሰብረዋል እሱም በግብፅ አምልኮተ ጣዖትን አጥፍቷልና።

የእግዚአብሔር ሰው የኾንክ አባታችን የተከበርክ #ማርስቆ ሆይ ዜናህ ወይም ዝናህ በምድር ሁሉ ላይ ተሰማ በኀይል ላይ ከእኛ ጋራ በአንድነት የሆንክ ስለእኛ ለምንልን።

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Nov, 08:00


#ቅዱስ_አባ_መቃርስ

ዳግመኛም በዚህች ቀን ቅዱስ አባት የሀገረ ቃው ኤጲስቆጶስ አባ መቃርስ አረፈ።

ለዚህም ቅዱስ የዝንጉዎችን ምክር ተከትሎ ያልሔደ በኃጢአተኞችም ጎዳና ያልተጓዘ በዘባቾችም መቀመጫ ያልተቀመጠ የእግዚአብሔርን ሕግ መጠበቅ ፈቃዱ የሆነ እንጂ ሕጉንም በቀንና በሌሊት የሚያነብ የሚያስተምር ብፁዕ ነው የሚለው የነቢይ ዳዊት ቃል ተፈጽሞለታል።

ይህ አባ መቃርስ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ በመጠበቅ በመክሊት ነግዶ ዕጥፍ አድርጎ አትርፎአልና እግዚአብሔርም በእጆቹ ያደረጋቸውን ታላላቆች ድንቆች ተአምራት ስንቱን እንናገራለን። ስለርሱም እንዲህ ተባለ እርሱ በሀገረ ቃው ተሾሞ በወንበር ተቀምጦ ሕዝብን በሚያስተምራቸው ጊዜ ዘወትር ያለቅሳል። ከደቀ መዛሙርቱም አንዱ እጅግ የሚወደው አማለውና አባቴ ሆይ ሁል ጊዜ ለምን ታለቅሳለህ ንገረኝ አለው እርሱም ስለ መሐላው ፈርቶ ዘይት በብርሌ ውስጥ እንደሚታይ የወገኖቼን ኃጢአታቸውን የከፋች ሥራቸውንም በማይና በምመለከት ጊዜ አለቅሳለሁ ብሎ መለሰለት።

ሁለተኛ ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመሠዊያው ላይ ተቀምጦ የየአንዳንዱን የሰውን ሥራ መላእክት ሲያቀርቡለት አየው በዚያንም ጊዜ እንዲህ የሚል ቃል ሰማሁ ኤጲስቆጶስ ሆይ ለምን ቸል ትላለህ ሕዝቡን አትገሥጻቸውምን አታስተምራቸውምን እርሱም አቤቱ እነርሱ ትምርቴን አይቀበሉም ብሎ መለሰ። ሁለተኛም እንዲህ አለው ለኤጲስቆጶስ ሕዝቡን ማስተማር ይገባዋል ትምርቱን ካልተቀበሉ ግን ደማቸው በራሳቸው ይሆናል።

ከዚህም በኋላ መናፍቁ ንጉሥ መርቅያኖስ ወደ ሰበሰበው ጉባኤ ከሊቀ ጳጳሳቱ ዲዮስቆሮስ ጋር ይሔድ ዘንድ ጠሩት የተሰበሰቡትም አንዱን ክርስቶስ ሁለት ባሕርይ የሚሉ ናቸው በደረሰም ጊዜ ስለ ልብሱ አዳፋነት ወደ ንጉሥ አዳራሽ መግባትን ከለከሉት አባ ዲዮስቆሮስም ከእርሱ ጋር እንዲአስገቡት ጳጳስ መሆኑን ነገራቸው።

በገቡም ጊዜ አንዱን ክርስቶስን ሁለት ባሕርይ አድርገው ትስብእቱን ከመለኮቱ እንደለዩት እምነታቸውን ሰሙ ስለዚህም ንጉሡንና ጉባኤውን አወገዙአቸው እሊህ አባቶቻችን አባ ዲዮስቆሮስና አባ መቃርስ ስለ ቀናች ሃይማኖታቸው ነፍሳቸውን ለሞት አሳልፎ ለመስጠት ቆርጠዋልና ንጉሡም ወደ ደሴተ ጋግራ አጋዛቸው።

ከዚያም ከምእመን ነጋዴ ጋር ወደ እስክንድርያ አባ ዲዮስቆሮስን ሰደደው እርሱ ለአባ መቃርስ ትንቢት ተናግሮለት ነበርና እንዲህ ብሎ አንተ ግን በእስክንድርያ አገር የሰማዕትነት አክሊል ትቀበል ዘንድ አለህ።

አባ መቃርስም ወደ እስክንድርያ ሲደርስ በዚያን ጊዜ የመናፍቁ የንጉሥ መርቅያን በውስጡ የከፋች ሃይማኖቱ የተጻፈበት የመልእክት ደብዳቤ ደረሰ መልእክተኛውንም እንዲህ ብሎ አዞታል በእኛ ሃይማኖት አምኖ በዚህ መዝገብ ውስጥ መጀመሪያ የጻፈ በእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ይሁን የሚል ነው አብሮታራ የሚባል አንድ ሰው ተቀዳድሞ በውስጡ ሊጽፍ ያንን መጽሐፍ ተቀበለ ቅዱስ አባ መቃርስም እንዲህ አለው ከእስክንድርያ አገር በሔደ ጊዜ ከእኔ በኋላ አንተ በቤተ ክርስቲያን የሠለጠንክ ትሆናለህ ብሎ የነገረህን የአባ ዲዮስቆሮስን ቃሉን አስብ ያን ጊዜ አብሮታራ ያንን ቃል አስታውሶ በዚያ በረከሰ መጽሐፍ ላይ ሳይጽፍ ቀረ።

የንጉሡም መልክተኛ አባ መቃርስ በንጉሥ ሃይማኖት እንደማያምን በአወቀ ጊዜ ተቆጥቶ ከኵላሊቱ ላይ ረገጠው ያን ጊዜም ሙቶ የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ ሥጋውንም ምእመናን ወስደው ከነቢይ ኤልሳዕና ከመጥምቁ ዮሐንስ ሥጋ ጋር በአንድነት አኖሩት ወደ ወደደው ክርስቶስም የመንግሥት ዘውድን ተቀዳጅቶ ሔደ።

#በረከቱ_ትደርብን_በቅዱሳኑ_ጸሎት_ይማረን
#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Nov, 07:55


#አባ_ጽጌ_ድንግል_ዘወለቃ

በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረ ሊቅ ሲኾን አባ ጽጌ ድንግል (ጽጌ ብርሃን) ሀገሩ ይፋት ሃይማኖቱ ኦሪት ነበረ፡፡ በንጉሥ ሰሎሞን ፈቃድና በካህኑ አዛርያስ መሪነት የብሉያት መጻሕፍትን ከዕብራይስጥ ወደ ግእዝ ተርጕመው ሊያስተምሩ፣ ታቦተ ጽዮንን ከኢየሩሳሌም ይዘው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡትና የብሉያት መጻሕፍት ሊቃውንት ከነበሩት ከ318 ሌዋውያን (ከቤተ እስራኤላውያን) ነገድ ነው፡፡ የተወለደውም በሰሜን ሸዋ በይፋት አውራጃ ውስጥ ሲሆን መጀመርያ ኢእማኒ (ያላመነና ያልተጠመቀ) ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ይህ ሰው በወጣትነት ዕድሜው አውሬ ለማድን ወደ ጫካ ሄደ ጫካዋም በዚያው በይፋት አውራጃ የምትገኝና ልዩ ስሟ ደንስ (ገዳመ ደንስ) ትባላለች በጫካዋ ውስጥም ፊቷ በጽጌረዳ አበባ የተከበበና ያጌጠ እጅግም ደስ የምታሰኝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል አይቶ በሥዕሏ ውበት እየተደነቀ ሥዕሏን ሲመለከት እንደ እርሱ ያልተጠመቀ ጓደኛው መጥቶ "ምን እየፈለግህ ነው? የክርስቲኖችን ሥዕል ነውን?" ብሎ ለድንግል ማርያም ምስጋና ይግባትና በያዘው በትር ሥዕሏን ሲመታት ወዲያው ተቀሥፎ ሞተ። ከዚህ በኋላ ክንፎቹ በጽጌረዳ አበባ ያጌጡ የመሰለ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በነጭ ወፍ ተመስሎ ወደ እርሱ መጥቶ አንድ ቀይ መነኩሴ እሰኪመጣ ድረስ ይህችን ሥዕል ጠብቃት ብሎ በሰው አነጋገር ነግሮት ተሠወረ።

የአቡነ ዜና ማርቆስ የገድል መጽሐፍ እንደሚናገረው ካህን ከነበረው ከአባቱ ከዘርዐ ዮሐንስ አና ከእናቱ ማርያም ዘመዳ በ1262 ዓ.ም ኅዳር 24 ቀን በሰሜን ሸዋ ግዛት በሚገኘውና ልዩ ስሙ እቲሳ ቅዱስ ሚካኤል በሚባለው አጥቢያ የተወለደው አቡነ ዜና ማርቆስ ደብረ ብሥራት ከሚባለው ገዳሙ ወደ ይፋት መጥቶ ከነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት 11፥1 ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ እያለ በግእዝ ቋንቋ ሲያነብ አባ ጽጌ ድንግል በሰማ ጊዜ አባቶቼ አይሁድ የነቢያትን ትንቢት ንባቡን አስተምረውኛል አውቀዋለሁ ትርጕሙን ግን አላውቀውምና ተርጕምልኝ አለው፡፡

አቡነ ዜና ማርቆስም ሲተረጕምለት እንዲህ አለ ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ የሚለው ንባብ ከእሴይ ነገድ የሕይወት በትር የኾነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትወለዳለች ማለት ነው፡፡ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ የሚለው ንባብ ደግሞ እመቤታችን ተወልዳ ከእርሷም ጌታ በድንግልና ይወለዳል ከጌታም ክብር ይገኛል ማለት ነው ይህም ጌታ ተወልዶ ትንቢቱ በእውነት ተፈጽሟል ብሎ ተረጐመለት፡፡ ኢሳ፡ 7፥14፣ ማቴ፡ 18፥24፡፡

ይህ ሰውም (አባ ጽጌ ድንግልም) በዚህ ትርጕም ደስ ተሰኝቶ አባት ሆይ የኢሳይያስን ትንቢት በመልካም ሁኔታ ተረጐምከው መልካም ነገርንም ተናገርክ አለውና ሥዕሏ ወዳለችበት ቦታ ወስዶ ታሪኩ ከላይ እንደተገለጸው በጫካ ውስጥ ያያትን ሥዕል ጓደኛው በያዘው ብትር ሲመታት ወዲያውኑ እንደተቀሠፈና ክንፎቹ በጽጌረዳ አበባ ያጌጡ "አንድ ነጭ ወፍ /ቅዱስ ሩፋኤል/" ወደ እርሱ መጥቶ ቀይ መነኵሴ እስኪመጣ ድረስ ይህችን ሥዕል ጠብቃት ብሎ በሰው አነጋገር ያነጋገረውን ሁሉ ነገረው አቡነ ዜና ማርቆስም ከሥዕሏ የተደረገውን ተአምር ሰምቶ እጅግ ደስ አለውና በል መጀመሪያ እመቤታችን በድንግልና በወለደችው በፈጣሪ ልጇ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን ይህችን ሥዕል ያስገኘ ሰማይና ምድርን በውስጣቸው ያለውንም ሁሉ የፈጠረ እርሱ እንደኾነ እውቅ አለውና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቆ ጽጌ ብርሃን ብሎ ሰየመው፡፡

ከዚህ በኋላ ሥዕሏን በገዳመ ደንስ ደብረ ብሥራት ወደሚባለው ገዳም ወስዶ በዘመነ ጽጌ ጥቅምት አንድ ቀን በክብር አስቀመጣት የምትከብርትንም ቀን ጥቅምት 3 እና ሰኔ 8 ቀን አደረገ፡፡

አቡነ ዜና ማርቆስም ጽጌ ብርሃንን ለመዓርገ ምንኵስና አበቃው፤ የአባ ጽጌ ብርሃንም ጽጌ ድንግል የሚል ቅጽል ስም አለው በማኅሌት አገልግሎት ጊዜም ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዜና ማርቆስ ቤተ ክርስቲያኒቱንና ሥዕሏን እየዞረ ሲያጥን እመቤታችን የካህናቱን አገልግሎት እንደምትባርክ ካህናቱ በግልጽ ይረዱ ነበር አባ ጽጌ ብርሃንም ከመጠመቁ በፊት በአባቶቹ በአይሁድ ሥርዓት እያለ የብሉያት መጻሕፍትን የተማረ ነበር የሐዲሳት መጻሕፍት ትርጓሜን ግን ከአቡነ ዜና ማርቆስ ተማረ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ላሉ አሕዛብ ሁሉ የድኅነት ምክንያት ትሆኑ ዘንድ ብርሃናቸው መምህራቸው አደረግኋችሁ ብሎ ጌታ ነቢዩ ኢሳይያስንና ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን እንደመረጣቸው ኢሳ 49፥6፤ ሐዋ፡ 13፥47

ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ዜና ማርቆስ ስብከተ ወንጌልን እንደ ዕለት ጉርስና እንደ ዓመት ልብስ አድርጎ መላ ኢትዮጵያን ዞሮ አስተምሮና ባርኮ የዕድሜ ባለጸጋም ሆኖ በተወለደ በ140 ዓመት በ1402 ዓ.ም ታኅሣሥ 3 ቀን ዐርብ ጠዋት ዐረፈ፡፡

አባ ጽጌ ብርሃንም በወሎ ክፍለ ሀገር በወራይሉ አውራጃ ልዩ ስሙ ደብረ ሐንታ ለሚባለው ገዳም የሕግ መምህር ሆኖ ከተሾመውና ከጓደኛው ከአባ ገብረ ማርያም ጋር እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንደ አንድ ልብ መካሪ በመሆን እመቤታችንንና ፈጣሪ ልጇን በጎ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየመሰለ የሚያመሰግነውን ማኅሌተ ጽጌ የተባለውን ድርሰት በአባቷ በዳዊት መዝሙር መጠን 150 አድርጎ ደረሰ፡፡ ፍሬ ከአበባ አበባም ከፍሬ እንደሚገኝ ኹሉ በማኅሌተ ጽጌ እመቤታችንን በአበባ ጌታችን በፍሬ ወይም እመቤታችንን በፍሬ ጌታችን በአበባ እየተመሰሉ የሚመሰገኑበት ምስጋና ነው። ሰቈቃወ ድንግል ማለት እመቤታችን ከልጇ ከመድኀኔዓለም ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር በስደቷ ወቅት ያየችውን መከራ ልቅሶ ዋይታ የሚዘከርበት የማኅሌተ ጽጌ አርኬ ነው፡፡

(የሰቈቃወ ድንግልን ደራሲ በተመለከተ አባ ጽጌ ድንግል ደረሱት የሚሉ አሉ በሌላ በኩል ደግሞ አባ ገብረ ኢየሱስ ዘገዳመ መጕና /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/ ወይም /አባ አርኬላዎስ/ ነው የደረሱት የሚሉም አሉ፡፡)

ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ የማያደርግ የሕግ ፍጻሜ ነውና ሮሜ 13፥10-11 አባ ጽጌ ብርሃንና አባ ገብረ ማርያምም የዘመነ ጽጌ የማኅሌት አገልግሎትን ሳይለያዩ በሰላምና በፍቅር (በአንድነት) አገልግለዋል ማለትም አንድ ዓመት አባ ገብረ ማርያም የክረምት መውጫና የዘመነ ጽጌ ዋዜማ በሆነው መስከረም 25 ቀን ከደብረ ሐንታ መጥቶ ገዳመ ጽጌ (ደብረ ብሥራት) ገብቶ ከመስከረም 26 ቀን እስከ ኅዳር 5 ቀን ያለውን የዘመነ ጽጌ የ40 ቀን አገልግሎትን ከአባ ጽጌ ብርሃን ጋር ፈጽሞ ኅዳር 8 ቀን ወደ ደብረ ሐንታ ይመለሳል በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ አባ ጽጌ ብርሃን ከገዳመ ጽጌ (ከደብረ ብሥራት) ወደ ደብረ ሐንታ ሄዶ እንደዚሁ እንደ አባ ገብረ ማርያም 40ውን ቀን አገልግሎ ይመለሳል እኒህ ሁለቱ ቅዱሳን ሊቃውንትም ታሪኩ ከላይ እንደተገለጸው እንዲህ እያደረጉ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው ድረስ በፍቅርና በትሕትና ሲያገለግሉ ኖረዋል፡፡

#በረከታቸዉ_ይደርብን

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Nov, 07:39


#መድኃኔዓለም

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእርጋታው የተነሣ "የተቀጠቀጠን ሸምበቆ አይሰብርም የሚጤስን የጧፍ ክርም አያጠፋም" ተብሏል ማቴ፡ 12፥20።
#የእርጋታ_መምህር_ነው።

"ከእኔም ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ" እንዲል ማቴ፡ 11፥29።
#የትሕትና_መምህር_ነው።

በመስቀል ተሰቅሎ ይቅርታን ለሰው ልጅ ያደለ እርሱ ነው። "ኢየሱስም አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው አለ" እንዲል ሉቃ፡ 23፥34።
#የይቅርታ_መምህር_ነው።

#የሰላም፣ #የፍቅር፣ #የትዕግሥት፣ #የሰማዕትነት በጠቅላላው የመልካም ሥራዎች ሁሉ መምህር እርሱ ነው።

እርሱን ሁልጊዜ ማሰብ ለነፍስ ዕረፍት ነው። እኛም ዋና አብነታችን እርሱ ስለሆነ መልካም ሥራዎችን ሁሉ አባታችንን እርሱን መስለን እንሥራ።

ለዚህች ልዩ ቀን እንኳን አደረሰን!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Nov, 07:23


#አቡነ_መብዓ_ጽዮን

ጥቅምት_27 ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት መታሰቢያ በዓል ጋር በታላቅ ድምቀት በየዓመቱ የምታከብራቸው ታላቅ አባት አሉ በ15ኛው መ.ክ.ዘ የነበሩትን አቡነ መብዓ ጽዮንን እግዚአብሔር አምላክ ቃልኪዳን የገባላቸውን ቀን በዓልን ሠርታ በታላቅ ድምቀት ታከብራቸዋለች ።

አቡነ መብዓ ጽዮን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን በዕለተ ዓርብ የተቀበልከውን መከራ ግለጽልኝ ብለው በጸለዩ ጊዜ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ የተቀበላቸውን መከራዎች ሁሉ አሳያቸው፡፡

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ ካዩበት ቀን ጀምሮ ኅማሙን መከራውን ግርፋቱን እስራቱን በጠቅላላ አስራ ሦስቱን ኅማማተ መስቀል በማሰብ ጀርባቸውን በአለንጋ ራሳቸውን በዘንግ ይመቱ ነበር።

የጌታችንን ኅማማተ መስቀል እያሰቡ ዘወትር ስለሚያለቅሱ ዐይናቸው ጠፍቶ ነበር ነገር ግን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የብርሃን ጽዋ ይዛ መጥታ ዐይናቸውን ቀብታ አድናቸዋለች።

ጥቅምት 27 ቀን ለአቡነ መብዓ ጽዮን ቃል ኪዳን የገባበት ቀን በመሆኑ በየዓመቱ ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዝክረ ጥንተ ስቅለቱ ጋር አብሮ ታስቦ ይከበራል፡፡

የጻድቁ አቡነ መብዓ ጽዮን በረከትና ረድኤት ይደርብን ሀገራችንን ኢትዮጵያን ጠላት ካሴረባት ሸፍጥ ሁሉ እግዚአብሔር አምላካችን ይታደጋት!



#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Nov, 07:19


#መድኃኔ_ዓለም

#ጥቅምት_27 ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የመድኃኔ ዓለምን በዓል በደማቁ ታከብራለች ይህም የለውጥ በዓል ነው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰው ሥጋውን የቆረሰው መጋቢት 27 ነው።

ነገር ግን መጋቢት 27 ቀን አቢይ ጾም ላይ ስለሚውል በዓቢይ ጾም ደግሞ ኀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለ በዓል ማክበርም ስለማይፈቀድ ወደ ጥቅምት 27 ተዛውሮ ደስ ብሎን ከድሆች ጋር እንድናከብረው ቤተ ክርስቲያን ሥርዓትን ሠርታልናለች።

በሞቱ ሞታችንን ያስወገደ፣ በኀዘኑ ኀዘናችንን ያራቀ በለቅሶው ዕንባችንን ያበሰ፣ ከወደቅንበት ያነሳን፣ ጠላታችንን ከመንገዳችን በመስቀሉ ጠርቆ ያስወገደ፣ በደሙ የቀደሰን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በአይሁድ ተንኮልና ክፋት በሓሰት ተወንጅሎ 6666 ጊዜ ተገርፎ 41 ጊዜ በብረት ዘንግ አናቱን ተመቷል።

በምራቁ እውር የሚያበራ ምራቅ ተተፋበት፤ ሥጋው አልቆ ደሙ ፈሶ አጥንቱ ይቆጠር ነበር ስለ ሁላችንም እርሱ ታመመ፤ ስለሁላችን እርሱ ሞተ መስቀል ተሸክሞ በኢየሩሳሌም ጎዳናዎች ወድቆ ተነሳ።

አይሁድ በወንጀለኛው በርባን ፋንታ ክርስቶስ ይሰቀል በርባን ይፈታ በማለት መድኃኒታቸውን ሰቀሉት ይሆን ዘንድ ግድ ነውና በቀራኒዮ አደባባይ በማዕከለ ምድር የዓለም መድኃኒት ተሰቀለ።

አይሁድ በውስጣቸው ባደረ ጠላት ዲያቢሎስ ምክንያት ክፋት ጭካኔያቸው የበዛ ሆነ #አዳኝ_መድኃኒት_ህ
ሕይወት_ፍቅር_ተስፋ የሆነውን ክርስቶስ በክፋት ተነሳስተው ቢሰቅሉትም ለእኛ ግን መዳን ሆነልን ሥጋውን በልተን ደሙን ጠጥተን የምንድን ሆንን።

በክርስቶስ ሞት ሞታችን ተወግዶ ሕይወት አገኘን በነፃነት እንኖር ዘንድ ነፃ አወጣን ተስፋችን መታመኛችን ኃይላችን እርሱ የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር የሆነ በመስቀል ሞት ነፃነታችንን አውጆ የዲያቢሎስ ክፋትና ተንኮል ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አስወግዶ #ተፈፀመ በማለት ነፍሱን ሰጠ

ዛሬ በቀደመው ክብሩ በዙፋኑ አለ ለማማለድ ሳይሆን ለመፍረድ አማላጅነት የአገልጋዮቹ የቅዱሳን ተግባር ነውና።

ጌታ ሆይ ወሰን ስለሌለው ፍቅርህ እናመሰግንሃለን🙏

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

03 Nov, 06:22


ኢትዮጵያዊቷ ገብረክርስቶስ ከጫጉላ ወጥታ የመነነችው ሙሽራዋ መናኝ ክርስቶስን በእንግዳ አምሳል የተቀበለችው ዳግማዊት ማርታ እና ሣራ ቅድስት ጸበለ ማርያም ጥቅምት 24 መታሰቢያዋ ነው በረከትዋ ይደርብን

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

03 Nov, 06:21


#ሦስቱ_የአቡነ_ተክለሃይማኖት_ምክሮች

ጻድቁ አባታችን ለአስር ዓመታት ያህል በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም በተጋድሎ ከቆዩ በኋላ መነኮሳትን ተሰናብተው ወደ ሌላ ቦታ በሚሄዱበት ጊዜ ለነፍሳቸው የሚጠቅማቸውን ምክር እንዲመክሯቸው በጠየቋቸው ጊዜ አባታችን ጻድቁ ተክለሃይማኖት እንዲህ በማለት ነበር የመከሯቸው

"ነገር ግን #ትዕግሥትን፣ $ትሕትናን፣ #እግዚአብሔርን_መፍራትን ገንዘብ አድርጉ፤ እነዚህ ሦስቱ ነገሮች ሰውን ወደ ዘለዓለም ሕይወት ያደርሱታልና። እየጎተቱ ወደ ደይን ጥልቅነት የሚያወርዱ ሦስቱ የጥፋት ገመዶች እነሱም #ቅናት፣ $ትዕቢትና #ትምክህት እንዳያጠምዷችሁ ደግሞ ተጠበቁ ብዬ እነግራችኋለሁ"

እንግዲህ እኛስ ከየትኞቹ ላይ ነው ምርጫችንና ትኩረታችን?? ወደ ዘለዓለም ሕይወት የሚያደርሱት ትዕግሥት፣ ትህትና፣ እግዚአብሔርን መፍራት ነው? ወይስ ወደ ደይን ጥልቅነት እየጎተቱ የሚጥሉና እሳቱ የማይጠፋ፤ ትሉ የማያንቀላፋ የዘለዓለም ስቃይና ቅጣትን የሚያመጡብን ቅናት፣ ትዕቢትና ትምክህት?

የጻድቁ አባታችን የአቡነ ተክለ ሃይማኖት በረከታቸው አይለየን ጸሎታቸው ይጠብቀን!!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

02 Nov, 07:54


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የአምስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

02 Nov, 07:53


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የአምስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

02 Nov, 07:52


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የአምስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

02 Nov, 07:51


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የአምስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

02 Nov, 07:50


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የአምስተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

31 Oct, 07:59


#ሦስቱ_አካላት_የተገለጡባት

በቅዱስ ገብርኤል የምሥራች ቃል ከድንግል ማርያም ሰው ኾኖ እንደተወለደ ትጠራጠራለህን፡፡ የቅዱስ ገብርኤል ጌታ ከእርሷ እንደተወለደ አታውቅምን ፡፡

ሰው የመኾኑን የምሥራች ይነግራት ዘንድ ባለሟሉን ወደ ሴት አገልጋዩ ላከ፡፡ እርሱም ደስ ይበልሽ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋራ ነው፡፡ እነሆ ትፀንሻለሽ ልጅም ትወልጃለሽ አላት፡፡ እርሷም ወንድ ሳላውቅ እንደ ምን ይኾንልኛል አለች፡፡ እነሆ የዳዊት ልጅ እውነትን መሠከረች፡፡ ከዚያን ጊዜ አስቀድሞ እንዲህ ያለ ፅንስ አልሰማችምና ስለዚህም መልዐኩ ካህኑ ዘካርያስን እንደ ነቀፈው አልነቀፋትም፡፡

መለአኩ መንፈስቅዱስ በ አንቺ ላይ ይመጣል አላት ለመለኮት ማደሪያ ትኾን ዘንድ በቅድስና የሚያከብር ከሥላሴ "አንዱ አካል" እነሆ። ኹለተኛም መልዐኩ የልዑል ኃይል ይጋርድሻል አላት የልጁ እናት ለመኾን የሚያጸናት ከሥላሴ "ሁለተኛው አካል እነሆ"፡፡ ዳግመኛም መልዐኩ ከአንቺም የሚወለደው ቅዱስ ነው የልዑል ልጅም ይባላል እግዚአብሔር አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል አላት ፡፡ ከድንግል የተወለደ "ሦስተኛ አካል" እነሆ ፡፡

ስለ መንፈስቅዱስ ባንቺ ላይ ይመጣል አለ ከአንቺ ሰው ይኾናል ግን አላለም፡፡ ስለ አብም የልዑል ኃይል ይጋርድሻል አለ ከአንቺ ይወለዳል ግን አላለም፡፡ እነሆ ከእርሷ የተወለደው ሦስተኛው ወልድ ነውና ስለ ወልድም ከአንቺም የሚወለደው ቅዱስ ነው፡፡ የልዑል ልጅም ይባላል፡፡ ከድንግል ስለ መወለዱም እግዚአብሔር አምላክ የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል አለ፡፡ ድንግል ማርያም ከዳዊት ወገን ናትና፡፡

#ዓመደ_ሃይማኖት_አባ_ጊዮርጊስ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

30 Oct, 05:47


#ኦልሳዕ_ነቢይ

ኤልሳዕ የስሙ ትርጒም “እግዚአብሔር ደኅንነት ነው” ማለት ነው፡፡ነቢዩ ኤልሳዕ እጅግ ባለጠጋ የሆነ ሰው ነበር።

ከዕለታት በአንደኛ ዕለት በ12 ጥማድ በሬ ሲያርስ ቴስቢያዊው ነቢዩ ኤልያስ ተከተለኝ አለው ምንም ሳያቅማማ ሀብት ንብረቱን ትቶ ተከተለው ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ከማረጉ በፊት ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ ቢለዉ ባንተ ላይ ያደረ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርብኝ ብሎታል እንደ ቃሉ ሆነለት ተደረገለት ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል።

የኤልያስ መንፈስ እጥፍ ድርብ ሆኖ አድሮበት ለረጅም ጊዜ እግዚአብሔርን አገለገለ ብዙ ተአምራትንም አደረገ፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ኢያሪኮ ከተማ በሚገባበት ጊዜ በከተማዋ የሚኖሩ ሰዎች ነቢዩ ኤልሳዕ ወደ እነርሱ እንደመጣ ባዩ ጊዜ “የዚች ከተማ ኑሮ መልካም ነው ውኃው ግን ክፉ ነው ምድሪቱም ፍሬዋን ትጨነግፋለች” አሉት የኢያሪኮ ከተማ ሰዎች ይህን ልመና ለኤልሳዕ ያቀረቡት እግዚአብሔር በቅዱሳኑ ነገርን ሁሉ መለወጥ እንደሚችል ይታመኑ ስለነበር ነው ነቢዩ ኤልሳዕ የሰዎቹን ችግር ከተረዳ በኋላ የከተማውን ሰዎች አዲስ ማሰሮ እና ጨው እንዲያመጡለት አዘዘ ሰዎቹም ኤልሳዕ እንዳዘዛቸው አደረጉ አዲስ ማሰሮ በውስጡ ጨው አድርገው አመጡለት ነቢዩ ኤልሳዕ ወደ ውሃው ምንጭ ወደ አለበት ስፍራ መጥቶ ጨው ጣለበት እና “እግዚብሔር እንዲህ ይላል ይህን ውኃ ፈውሼዋለሁ ከዚህም በኋላ ሞትና ጭንጋፉ አይሆንበትም” ብሎ ለከተማው ሰዎች ተናገረ ኤልሳዕም እንደ ተናገረው ውኃው እስከ ዛሬ ድረስ ተፈውሷል የኢያሪኮ ከተማ ሰዎች ከዛ ጊዜ ጀምሮ ንጹሕ ውኀ መጠጣት ጀመሩ የምድሪቱንም ፍሬ ተመገቡ እግዚአብሔር በነቢዩ አልሳዕ ድንቅ ነገር ሰላደረገላቸው ዘወትር ያመሰግኑ ነበር፡፡

እምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳዕ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች።

የዚህ ነቢይ ድንቅ ታሪኩ 2ኛ ነገሥት 19 ላይ በስፋት ተጽፏል ጥቅምት 20 ልደቱ ሲሆን ሰኔ 20 ቀን ደግሞ በዓለ ዕረፍቱ ነው።

#በዓሉ_በእንጦጦ_ራጉኤል_ይከብራል።

#የነቢዩ_ኤልሳዕ_በረከት_ይደርብን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

29 Oct, 12:20


የሰማዕቱ የቅዱስ እስጢፋኖስ በዓል ሲመት አከባበር በካራ ቆሬ ደብረ ገነት ቅዱስ እስጢፋኖስ ቅዱስ ሚካኤል እና ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅንጭብ ቪዲዮ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

28 Oct, 07:33


#ቅዱስ_እስጢፋኖስ

እንኮን ለቀዳሜ ሰማዕት ለቅዱስ እስጢፋኖስ በዓለ ሹመት በሰላም አደረሳቹህ።

እስጢፋኖስ ማለት ‹‹መደብ›› ማለት ሲሆን በግሪክ ቋንቋ ‹‹አክሊል›› ማለት ነው፡፡ በግብሩ የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር የማይለውጠው መብራት ማለት ነው ትውልዱ ከነገደ ብንያም ሲሆን አባቱ ስምዖን እናቱ ሐና ይባላሉ እነርሱም እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ከነቢያትና ከጻድቃን ወገን ናቸው በመጀመሪያ ሁለት ወንድ ልጆችን ወለዱ አንዱ ይሁዳ ሲባል ሁለተኛውም ቅዱስ እስጢፋኖስ (አስተፓኖስ) ነው፡፡

እስጢፋኖስ የተወለደው ጥር 1 ቀን በእስራኤል ሀገር ውስጥ ልዩ ስሟ ሐኖስ በተባለች ቦት ነው የተወለደውም በስለት ነው እርሱም ከመጥምቁ ዮሐንስ እግር ሥር በመሆን ተምሯል በኋላም ወደ ቅዱሳን ሐዋርያት በመሄድ ይላላካቸውና ያገለግላቸው ነበር በኢየሩሳሌም ቤተ ክርስቲያን ከተሾሙት ከ7ቱ ዲያቆናት አንዱ ሲሆን የዲያቆናት አለቃ እርሱ ነው ቅዱስ እስጢፋኖስ ወንጌልን በማስተማሩና ብዙዎችን ክርስቶስን ወደማመን ስለመለሳቸው ክፉዎች አይሁድ በጠላልትነት ተነስተውበት ጥር 1 ቀን በ34 ዓ.ም ከጌታችን ቀጥሎ ከምእመናን ወገን የመከራውን ገፈት ስለተቀበለ (በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ስላረፈ) ‹‹ቀዳሜ ሰማዕት›› ተሰኘ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ›› እየተባለ ይጠራል፡፡ ይኸውም የከበሩ ቅዱሳን ሐዋርያት በሰባቱ ዲያቆናት ላይ አለቃ አድርገው በሾሙት ጊዜ የተሰጠው ስያሜ ነው፡፡

የመጀመሪያ ክርስቲያኖች የአማኞች ቊጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በሄደ ጊዜ የማኅበራዊው ኑሮ አስተዳደር ማለትም የምግብንና የመሳሰሉትን ቁሳቁሶች (ገንዘብም ጭምር) በትክክልና በእኩልነት የማከፋፈሉ ሥራ በሐዋርያት ዘንድ አስቸጋሪ ሆኖ ተገኘ እነርሱም ደግሞ ዋና ተግባር አድርገው በትጋት ለመያዝ የፈለጉት ማስተማርን ነበር ስለዚህም አማኞችን ሁሉ ሰብስበው ከመካከላቸው በመልካም ጠባያቸው የተመሰገኑ በመንፈስ ቅዱስና በጥበብ የተሞሉ ሰባት ሰዎችን እንዲመርጡ አሳስቧቸው አማኞችንም ነገሩ አስደስቷቸው ሰባት ሰዎችን መረጡ፡፡

እነርሱም፡- ቅዱስ እስጢፋኖስ (ዕረፍቱ ጥር 1)፣ ቅዱስ ጵሮኮሮስ (ሰኔ 8)፣ ቅዱስ ጢሞና (ሚያዝያ 16)፣ ቅዱስ ፊልጶስ (ጥቅምት 14)፣ ቅዱስ ጰርሜና (መስከረም 1)፣ ቅዱስ ኒቃሮና (3 ጊዜ ሞቶ የተነሣ)፣ ቅዱስ ኒቆላዎስ (ሚያዝያ 15) ናቸው፡፡

የሰባቱ ዲያቆናት ረድኤት ይልቁንም የቀዳሜ ሰማዕት ሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ በረከት አይለየን።


#ትላንት_በአገልግሎት_ተጠምጄ_ስላልጻፍኩላችሁ_ዛሬ_ማስታወስ_ይገባልና_ነዉ

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Oct, 05:37


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የዐራተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Oct, 05:35


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የዐራተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Oct, 05:33


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የዐራተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Oct, 05:30


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የዐራተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Oct, 05:27


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የዐራተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

26 Oct, 04:15


🌹🌹#ብኪ_ይወጽኡ_ኀጥአን_አምደይን🌹🌹

🌹#ኀጥንም_ባንቺ_ምልጃ_ከእሳት_ይወጣሉ🌹

እመቤታችን ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ ሆና በፈጣሪና በፍጡራን መካከል የነበረውን ጠብ ለማብረድ የተፈጠረውን ክፍተት ለማስወገድ ያዘጋጃት መቀራረቢያ መታረቂያ ምልክት ናት።

አባ ጽጌ ድንግል እንዲህ ሲል ያመሰግናታል ‹‹ በፈጣሪና በፍጡራን መካከል ለዕረፍት የቃል ኪዳን ምልክት የሆንሽ ፤ የብርሃን ቀን ሰንበተ ሰንበታት ማርያም ሆይ አበባ ባለበት ገነት ያሉ ጻድቃን በአንቺ ደስ ይላቸዋል ኀጥአንም በአንቺ ከደይን ይወጣሉ፡፡ ›› በማለት እመቤታችን ፈጣሪና ፍጡራን የታረቁባት የዕርቅ ሰነዳችን ፤ በፍዳ በኵነኔ ደክመው ተጎሳቁለው የነበሩ የሰው ልጆች ዘለዓለማዊ ዕረፍት ያገኙባት የዕረፍት ቀናችን ናት።

ለዚህም ምስክራችን በላኤ ሰብ ነው በላኤ ሰብ በምድር ብዙ ነፍስ አጥፍቶ የበላኤ ሰብእ ነፍስ በፈጣሪ ፊት ለፍርድ በቆመች ጊዜ የመጀመሪያው ፍርድም ‹‹ ይህቺን ነፍስ ወደ ሲዖል ውሰዷት ›› የሚል ነበር እመቤታችንም ‹‹ ይህችን ነፍስ ማርልኝ ›› ስትል ልጇን ወዳጇን ለመነችው።

በላኤ ሰብእ ያጠፋቸው ነፍሳትና የሰጠው ጥርኝ ውኃ በሚዛን በተመዘነ ጊዜ በመጀመሪያም የበላኤ ሰብእ ጥፋት መዘነ ነገር ግን እመቤታችን ቃል ኪዳኗ ባረፈበት ጊዜ ጥርኝ ውኃው ሚዛን ደፋ።

የበላኤ ሰብእ ነፍስ በእመቤታችን አማላጅነት ዳነች ይህም የእግዚአብሔር ቸርነት የሚያሳይ ነው አስቀድሞም በወንጌልም በደቀ መዝሙር ስም ብቻ ቀዝቃዛ ውኃ ያጠጣ ዋጋው አይጠፋበትም ማቴ ፦10÷42 የሚለው ቃል ተፈጸመ፡፡

እመቤቴ ሆይ ያለ አንቺ እውቅና ያለ አንቺ ምልጃ ወደ እግዚአብሔር የሚደረግ ልመናና ጸሎት ዕጣንና ቁርባን የለምና እኛን ልጆችሽን በቃል ኪዳንሽ ከልጅሽ ከወዳጅሽ አማልደሽ አስምሪን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

24 Oct, 05:44


“#እስጢፋኖስም_ጸጋንና_ኃይልን_ተሞልቶ_በሕዝቡ_መካከል_ድንቅንና_ታላቅ_ምልክትን_ያደርግ_ነበር።” ሐዋ 6፥8

#ታላቅ_የንግስ_በዓል_እና_ልዩ_መንፈሳዊ_ጉባዔ_ጥሪ

በደብራችን በካራ ቆሬ ደብረ ገነት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ #ቅዱስ_ሚካኤል እና #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ቤተ ክርስቲያን የፋታችን ጥቅምት ፲፯ #የሰማዕቱ_የቅዱስ_እስጢፋኖስን_በዓለ_ሲመት ብጹአን አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት የሀገረ ስብከታችን እና የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ተወካዮች የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ይከበራል በዓሉንም ምክንያት በማድረግ ከጥቅምት 16 እስከ 21 የሚቆይ ተከታታይ ልዩ መንፈሳዊ ጉባዔ ከደብራችን ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በጋራ በመሆን ተዘርግቷል ስለሆነም ኦርቶዶክሳውያን ሁላችሁም በበዓሉ ላይ በመገኘት የእግዚአብሔርን በረከት ታገኙ ዘንድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

አድራሻ ከፒያሳ፤ መርካቶ፤ አቶቢስ ተራ፤ሜክሲኮ:-  አየርጤና ካራ ቆሬ ከረጲ ትምህርት ቤት ጀርባ ደግነት ኮንደሚንየም በተለምዶ ስሙ ጥላሁን ሜዳ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

24 Oct, 05:37


#በዓለ_ዕረፍቱ_ለዲያቆን_ፊልጶስ_ቅዱስ

ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ፊልጶስ ነው በዚህ በጥቅምት 14 ቀን ዓመታዊ በዓለ እረፍቱ የሚታሰብበት ወቅት ነው በሐዋርያት አሳሳቢነት ማኅበረ ምእመናንን እንዲያገለግሉ ከተመረጡት ሰባት ዲያቆናት አንዱ ነው። ሐዋ፡ 6፥5 መኖሪያው በቂሣርያ ሲሆን ባለትዳርና የአራት ሴቶች ልጆች አባት ነው፡፡

ወደ ሰማርያ ወርዶ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን ከአምልኮተ ጣዖት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሷል። ሐዋ፡ 21፥8 የሀገራችንን ጃንደረባ ባኮስን አስተምሮ ያጠመቀው ይኽው ዲያቆን ፊልጶስ ነው ብዙ መከራ እየተቀበለ ለብዙዎች የመዳን ምክንያት ሆኗል።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሐዋርያ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለም ትኑር !

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

24 Oct, 05:31


#መናኙ_ሙሽራ_ጻድቁ_ገብረ_ክርስቶስ

ጥቅምት 14 ቀን #የጻድቁ_የገብረ ክርስቶስ_የዕረፍቱ_በዓል_ነው

#የጻድቁ_የገብረ_ክርስቶስ አባቱ ቴዎዶስዮስ እናቱ መርኬዛ ይባላሉ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምግባር ትሩፋት የሚሠሩ በማኅበረ ሰባቸው ዘንድ የተከበሩ ደጋግ ሰዎች ነበሩ።

ልጅ አልነበራቸውም ነበርና በዚህ ያዝኑ ነበር ወደ እግዚአብሔር ጸለዩ እግዚአብሔርም ጸሎታቸውን ሰምቶ ልጅ ሰጣቸው ስሙንም አብደልመሲህ አሉት ትርጓሜውም ገብረ ክርስቶስ ማለት ነው።

#ገብረ_ክርስቶስም በሃይማኖት በምግባር ተኮትኩቶ አደገ ለአቅመ አዳም ሲደርስ ለሮሜ ንጉሥ ልጅ አጋቡት #ገብረ_ክርስቶስ ግን ምኞቱ ሰማያዊ ሙሽራ መሆን እንጂ በዚህ ምድር አግብቶ የመኖር ሐሳብ አልነበረውምና ሌሊት ሙሽራዋን እግዚአብሔር ይጠብቅሽ ብሉ መርቆ ንጽሕናውን ጠብቆ ጥሏት መነነ፡፡

ወላጆቹም ያስፈልጉት ጀመረ እርሱ ግን በገድል በትሩፋት በጾም በጸሎት ሰውነቱ እጅግ ተጎሳቁሎ መልኩ ተለውጦ ስለነበር ሊያገኙት አልቻሉም የእኔ ቢጤ መስሎ ከወላጆቹ ቤት በር ላይ ተቀመጠ።

እጅግ ቆሳስሎ ስለነበር የአባቱ ባሮች ይሰድቡት ያንቋሽሹት ነበር ቆሻሻ ውኃም ውሾች እንዲናጠቁበትም የሥጋ ፍርፋሪ ይጥሉበት ነበር የድስት እጣቢም ያፈሱበት ነበር።

ይህ ሁሉ ሲሆን ልጃቸው መሆኑን አላወቁም በኋለ ግን 15 ዓመት በደጃቸው ሲንገላታ ኖሮ ሊሞት ሲል ገድል ትሩፋቱን ታሪኩን ጽፎ በእጁ ይዞ ከዚህ ዓለም በሞት ተሰናበተ ወላጆቹም ያችን ደብዳቤ አነበቧት ልጃቸው መሆኑን አወቁ ታላቅ ጩህት ሆነ መሪር ልቅሶ አለቀሱ በክብርም ቀበሩት።

የጻድቁ የገብረ ክርስቶስ ሙሽራ ረድኤት በረከቱ በሁላችንም ላይ አድሮ ለዘላለም ይኑር !

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

24 Oct, 05:31


#በምድር_መንነሃልና_በደስታ_ከዚህ_ዓለም_ድካም_አሳርፍሃለሁ

#ጻድቁ_አባታችን_አቡነ_አረጋዊ_ጥቅምት_14_ቀን በ 99 ዕድሜያቸው በጾም በጸሎት በተጋድሎ ከኖሩበት ገዳም በእግዚብሔር ጸጋ እንደ ሔኖክና እንደ ኤልያስ ከሞት ገጽ የተሠወሩበት ዓመታዊ የመታሰቢያ ቀናቸው ነው ።

ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ መንፈሳዊ አገልግሎት ካበረከቱ ቅዱሳን አባቶች መካከል አንዱ ጻድቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ ናቸው።

የኢትዮጵያ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም የማይዘነጋ ዘለዓለማዊና ሰማያዊ ውለታቸውን አስባ በስማቸው ጽላት ቀርጻ ቤተ ክርስቲያን ሰይማ ገድላቸውንና ተአምራታቸውን ጽፋ ቅዱስ ብላ ታከብራቸዋለች።

በየወሩና በየዓመቱ ዕረፍታቸውን ( ዕርገታቸውን ) ታዘክራለች ! በቃል ኪዳናቸውና በስማቸውም ፈጣሪዋን ትማጸናለች።

ጻድቁ አቡነ አረጋዊ በ5ኛው ክፍለ ዘመን ( 460 ዓ.ም ) በመንግሥተ አልአሜዳ የሮማ ግዛት ከሆኑት ከሶርያና ከቁስጥንጥንያ እንዲሁም ከተለያዩ ሀገሮች ወደ ኢትዮጵያ ከመጡት ዘጠኝ ቅዱሳን አንዱ ናቸው።

እነዚህን ስምንቱን ቅዱሳንን ወደ ኢትዮጵያ እንዲመጡ መንገድ የመሯቸው እኚህ ጻድቅ አባት ናቸው ዘጠኙ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ የመጡበት ዐቢይ ምክንያት በጉባዔ ኬልቄዶን በ451 ዓ.ም መለካውያን ባነሡት የክሕደት አመፅ የኹለት ባሕርይ እምነት አንቀበልም በማለታቸው የቢዛንታይን መንግሥት የቁም ስቃይ ስላጸናበቸው ነበር

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በወንጌሉ ‹‹ ከአንዱ ሀገር ቢያሳድዷችሁ ወደ ሌላው ሽሹ ›› ያለውን መለኮታዊ ቃል ተገንዝበው በእምነትና በአምልኮት ወደሚመስሏቸው ሀገራት ጥግ ፍለጋ ተሰደዋል።

አቡነ አረጋዊ በትውልድ ሀገር ሮማዊ ናቸው አባታቸው በሮም ከነገሡ ነገሥታት አንዱ ሲሆኑ ስማቸውም ‹ ይስሐቅ › ይባላል እናታቸው ‹ አድና › ይባላሉ እግዘአብሔርን የሚፈሩ በማኅበረሰባቸው ዘንድ የተከበሩ ነበሩ።

አቡነ አረጋዊ ከመምህራቸው ከአባ ጳኩሚስ ዘንድ ሥርዓተ ማኅበርን እንዲሁም ሥርዓተ ምንኵስናን ተምረው ገዳማዊ ሕይወትን ከመሠረቱት ከአባ እንጦንስ በአራተኛ ደረጃ የሚታወቁ ታላቅ አባት ናቸው።

አቡነ አረጋዊ ሦስት ስሞች አላቸው ! አንደኛው ወላጆቻቸው ያወጡላቸው ‹‹ ገብረ አምላክ ›› የሚለው ነው ! ኹለተኛው መምህራቸው አባ ጳኩሚስ ያወጡላቸው የምንኩስና ስማቸው ‹‹ ዘሚካኤል ›› የሚለው ነው።

ሦስተኛው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ በኋላ ስምንቱ አኀው ያወጡላቸዉ ‹‹ አረጋዊ ›› የሚለው ስም ሲሆን በኢትዮጵያ መጠሪያ ስማቸው ሆኖ ቀርቷል።

እነዚህ ዘጠኝ ቅዱሳን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በአት መሥርተው ገዳማትን አቅንተው ወንጌልን ሰብከዋል ሥርዓተ ምንኩስናንና ገዳማዊ ሕይወትን አስተምረዋል።

ከገድላቸው መካከል ጎልቶ የሚታወቀው በቅዱስ ሚካኤል ተራዳዒነት በዘንዶ ኀይል ደብረ ዳሞን ተራራ ወጥተው መኖራቸው ነው።

ይህም የዘንዶውን ጅራት በመያዝ ከደብረ ዳሞ ተራራ ላይ ወጥተው በዚያ ፍጹም ተጋድሎ ፈጽመዋል፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ስማቸውን ለሚጠራ መታሰቢያቸውንም ለሚያደርግ ሁሉ ምሕረትን እንደሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጥቷቸው ጥቅምት 14 ቀን በ 99 ዕድሜያቸው በጾም በጸሎት በተጋድሎ ከኖሩበት ገዳም በእግዚብሔር ጸጋ እንደ ሔኖክና እንደ ኤልያስ ከሞት ገጽ ተሠውረዋል።

በመጨረሻም ‹‹ መንፈስ ቅዱስ ከሰማይ መጣ ጸሎትህን ሰምቻለሁ ብዙ የሆነ ትዕግሥትህን አይቻለሁ ድውያንን ትፈውስ ዘንድ ስልጣን ሰጥቼሃለሁ የታመሙት ሁሉ ይድናሉ ለምጻሞች በቃልህ ይነጻሉ በምድር መንነሃልና እነሆ በደስታ ከዚህ ዓለም ድካም አሳርፍሃለሁ ወደ ዘለዓለም ሕይወት ትሔዳለህ። ›› ብሏቸው ከዐይነ ሞት ተሠወሩ።

ቸር የዋህ እግዚአብሔርን የምትፈራ አባታችን አቡነ አረጋዊ ሆይ ! ስለእኛ ጸልይ ! አቤቱ አምላካችን ሆይ አባቶቻችን አንተን ተማመኑ ተማምነውም አዳንካቸው ወደ አንተ ጮኹ ዳኑም አንተንም ተማመኑ አላፈሩም የሰማያትን ሙሽርነትን አስቀድመው ስለአንተ ነፍሳቸውን ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋልና ስለተጋድሏቸውና ስለጽኑዕ እምነታቸው ስትል ማረን ይቅር በለን!

#የአቡነ_አረጋዊ_ረድኤት_በረከታቸው_ይደርብን_በጸሎታቸው_ይማረን !

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

23 Oct, 19:54


“#እስጢፋኖስም_ጸጋንና_ኃይልን_ተሞልቶ_በሕዝቡ_መካከል_ድንቅንና_ታላቅ_ምልክትን_ያደርግ_ነበር።”
ሐዋ 6፥8

#ታላቅ_የንግስ_በዓል_እና_ልዩ_መንፈሳዊ_ጉባዔ_ጥሪ

በደብራችን በካራ ቆሬ ደብረ ገነት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ #ቅዱስ_ሚካኤል እና #ቅድስት_ድንግል_ማርያም ቤተ ክርስቲያን የፋታችን ጥቅምት ፲፯ #የሰማዕቱ_የቅዱስ_እስጢፋኖስን_በዓለ_ሲመት ብጹአን አባቶች ሊቃነ ጳጳሳት የሀገረ ስብከታችን እና የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ተወካዮች የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ይከበራል በዓሉንም ምክንያት በማድረግ ከጥቅምት 16 እስከ 21 የሚቆይ ተከታታይ ልዩ መንፈሳዊ ጉባዔ ከደብራችን ሰንበት ትምህርት ቤት ጋር በጋራ በመሆን ተዘርግቷል ስለሆነም ኦርቶዶክሳውያን ሁላችሁም በበዓሉ ላይ በመገኘት የእግዚአብሔርን በረከት ታገኙ ዘንድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጥሪዋን ታስተላልፋለች።

አድራሻ ከፒያሳ፤ መርካቶ፤ አቶቢስ ተራ፤ሜክሲኮ:- አየርጤና ካራ ቆሬ ከረጲ ትምህርት ቤት ጀርባ ደግነት ኮንደሚንየም በተለምዶ ስሙ ጥላሁን ሜዳ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

22 Oct, 16:45


ለመፍታት ዕድል ስጡ፡፡ በእግዚአብሔር ስም ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንና ልጆቻችን የምናስተላፈው ወቅታዊ መልእክታችን ይህ ነው፡፡ 

በመጨረሻም
በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሁለንተናዊ አገልግሎትና የስራ አፈጻጸም ላይ ለመምከርና ለመወሰን ኃላፊነት ያለው ቅዱስ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት መደበኛና ዓመታዊ ጉባኤውን የጀመረ መሆኑን ለሕዝበ ክርስቲያኑ እናበስራለን፡፡
እግዚአብሔር ጉባኤያችንን ይባርክ!
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን::

      አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ፤

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

22 Oct, 16:45


መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

•ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጐጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
•ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤
ዓመቱን ጠብቆ ስለ አጠቃላይ ተልእኮአችን ለመወያየት በዚህ ጉባኤ የሰበሰበን አምላካችን ስሙ የተመሰገነ ይሁን፤
“ወይእዜኒ ግብኡ ኀበ ኖላዊሃ ወዓቃቢሃ ለነፍስክሙ፤ አሁንም ወደ እረኛችሁና ወደ ነፍሳችሁ ጠባቂ ተመለሱ” (1 ጴጥ 2÷!5)
ሁሉን የሚችል አምላካችን እግዚአብሔር በፍቅሩና በፍቅሩ መነሻነት ብቻ ፍጥረታትን በሙሉ እንደፈጠረ ቅዱስ መጽሐፍ ያስተምረናል፤ ከፈጠረም በኋላ የክብሩ ተሳታፊ እንዲሆኑ ወዶ ክብሩን አድሎአቸዋል፡፡ እግዚአብሔር ለፍጡራኑ ካደላቸው ነገሮች አንዱ በየዓይነታቸው ጠባቂና መሪ እያደረገ በፍጡራን ላይ ፍጡራንን መሾሙ ነው፤ ይህ ስጦታ በሰማይም ሆነ በምድር ላሉ ፍጥረታት የተሰጠ የሱታፌ መለኮት ስጦታ ነው፡፡
ይህም በመሆኑ ሁሉም ፍጡራን አራዊትም ሆኑ እንስሳት ይብዛም ይነስ ጠባቂና መሪ እንዳላቸው እናስተውላለን፤ በተለይም የፍጥረታት ቁንጮ የሆኑ መላእክትና ሰዎች መሪና ሹም እንዳሏቸው የማንክደው ሓቅ ነው፡፡ ቅዱስ መጽሓፍም ይህንን ደጋግሞ ያስረዳል፤ የእነዚህ ሁሉ ላዕላዊ ጠባቂና መሪ ደግሞ እግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በፍጡራን ላይ ፍጡራንን ጠባቂዎች አድርጎ ሲሾም ፍጡራንን የክብሩ ተሳታፊ ለማድረግ እንጂ የእሱ ጥበቃ አንሶ ወይም ድጋፍ ሽቶ አይደለም፡፡ ስለሆነም ፍጹምና ላዕላዊ የሆነ ጥበቃው ሁሉንም ያካለለ ነውና ከእሱ ቊጥጥርና ጥበቃ ውጭ አንድም ነገር እንደሌለ የምንስተው አይደለም ፡፡

•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
•የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በአምሳለ እግዚአብሔር በተፈጠረውና በክብር መልዕልተ ፍጡራን በሆነው ሰው ላይ በዚህ ዓለም የተሾሙ ሁለት አካላት አሉ፤ እነሱም የመንፈስና የዓለም መሪዎች ናቸው፡፡  በተለይም የመንፈስ መሪዎችና ጠባቂዎች የተባሉት በመንፈስ ቅዱስ ተሹመን በዚህ ክርስቶሳዊ ጉባኤ የተሰበሰብነው እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ነን፡፡
ይህ ጉባኤ በሀገር ውስጥና በውጭ ለሚገኙና በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን መሪና ጠባቂ ነው፤ ከዚያም ባሻገር እንደ ቃሉ እስከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ቃሉን በመስበክ ፍጥረተ ሰብእን በሙሉ የመጥራት ተልእኮ ለእኛ የተሰጠ የቤት ስራ ነው፡፡ ከዚህ አኳያ የተሰጠን ኃላፊነት እጅግ በጣም ታላቅ እንደመሆኑ የሚጠበቅብን ውጤትም በዚያው ልክ ትልቅ ነው፤ ብዙ ከተሰጠው ብዙ ይፈለግበታል ያለው የጌታችን አስተምህሮም ይህንን ያስታውሰናል፡፡

ሁላችን እንደምንገነዘበው አሁን የምንገኝበት ዘመን የጸላኤ ሠናያት መንፈስ በእግዚአብሔር ሕዝብ ላይ ከምንም ጊዜ በበለጠ ጦሩን ሰብቆ የተነሣበት ጊዜ ነው፤ አሁን ያለው ዓለም በሀገራችንም ሆነ በሌላው ክፍለ ዓለም ላሉ ኦርቶዶክሳውያን ከባድ ፈተና ደቅኖብናል፡፡ ክፉው መንፈስ የሰውን አእምሮ በማዛባት ምእመናንን በቅዱስ መጽሐፍና በሕገ ተፈጥሮ ከተመደበላቸው የጋብቻ ሕግ በማስወጣት እንስሳት እንኳ የማይፈጽሙት ነውረ ኃጢአት እንዲፈጽሙ በመገፋፋት ላይ ይገኛል፡፡ በአማንያን ልጆቻችን ላይም በረቀቀ ስልት ግድያ፣ እገታ፣ አፈና፣ የመብት ተጽዕኖ እና አድልዎ በማድረግ እንደዚሁም በአስመሳይ ስብከትና አምልኮ ጣዖትን በማለማመድ ሕዝቡ ሳይገባውና ሳይጠነቀቅ ከእግዚአብሔር መንግሥት እንዲወጣ እያደረገ ነው፡፡

•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
•የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
ክፉው መንፈስ በተራቀቀና በተራዘመ ስልት ሊውጠን በተነሣ ልክ እኛም ከእሱ እጥፍ በሆነ መለኮታዊ ኃይል ልንመክተው ካልቻልን በፈጣሪም ሆነ በትውልድ እንደዚሁም በታሪክ ፊት በኃላፊነት መጠየቃችን አይቀርም፡፡ መከላከል የምንችለውም ችግሩን በውል ከመረዳት አንሥቶ ሕዝቡን በደምብ በማስተማርና በመጠበቅ እንደዚሁም ለመሪነታችን ዕንቅፋት ከሚሆኑን ዓለማዊ ነገሮች ራሳችንን በማራቅ ነው፡፡ ሕዝቡም በዚህ ዙሪያ ሊያደምጠንና ሊከተለን የሚችለው መስለን ሳይሆን ሆነን ስንገኝለት ነው፡፡ ሕዝቡ ሊከተለን የሚችለው እሱን በብቃት ለመጠበቅ ዓቅሙም ተነሣሽነቱም ቁርጠኝነቱም እንዳለን ሲመለከት፣ እንደዚሁም ከዕለት ተዕለት ተግባራችንና አኗኗራችን የሚያየው ተጨባጭ እውነታ ኅሊናውን ሲረታ እንደሆነ አንርሳ፡፡

የምናስተምረው ሌላ የምንሰራው ሌላ ከሆነ ግን ከሕዝቡ አእምሮ መውጣታችን እንደማይቀር መገንዘብ አለብን፤ በመሆኑም በሰብእናችን፣ በአስተዳደራችን፣ በአመራራችንና በጥበቃችን ሁሉ እንደቃሉና እንደቃሉ ብቻ ለመፈጸም መትጋትና በቁርጥ መነሣት ጊዜው አሁን ነው እንላለን፡፡ ይህ ሲሆን በምእመናንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት አስተማማኝና እንከን የለሽ ይሆናል፤ ይህ ከሆነ እውነትም የመሪነት፣ የእረኝነትና የመልካም ተምሳሌነት ኃላፊነታችንን በትክክል ተወጥተናል ማለት እንችላለን፡፡

•ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
•የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
  የሰው ልጆች በዚህ ዓለም ሲኖሩ የተሟላ ሰላምና ጣዕመ ሕይወት ሊኖራቸው የሚችለው በመንፈሳዊ ኑሮአቸው የተሻለ ነገር ስላገኙ ብቻ አይደለም፡፡ ሰዎች ከሥጋዊ ክዋኔም ጭምር የተፈጠሩ እንጂ እንደመላእክት ሥጋ የሌላቸው መንፈስ ስላይደሉ ለኑሮአቸውና ለሥጋዊ ክዋኔአቸው የሚሆን ነገር ያስፈልጋቸዋል፡፡ በዚህም ዓለማዊው አስተዳደር የተመቻቸ መደላድል ሊፈጥርላቸው ግድ ነው፤ ዓለማዊው አስተዳደርም የመለኮትን ተልእኮ ለመፈጸም የተሾመ ሹመኛ እንደመሆኑ የእግዚአብሔርን ሕዝብ በትክልል መምራት ይጠበቅበታል፡፡ ምንም ቢሆን የተቀበለው ኃላፊነት የእግዚአብሔር ነውና በሚሰራው ሁሉ በሿሚው አምላክ ከመጠየቅ አያመልጥም፡፡

እኛም በዚህ ዓለም የእግዚአብሔር ወኪሎች ስለሆንን ቢሰሙንም ባይሰሙንም ዓለማውያን ሹማምንትን  የማስተማርና የመምከር ኃላፊነት አለብን፡፡ ይህ የሁለታችን ኃላፊነት እንደ እግዚብሔር ፈቃድ ስንፈጽም የሕዝብ ሰላምና በረከት፣ ፍቅና አንድነት፣ ዕድገትና ልማት በአስተማማኝ ሁኔታ ይረጋገጣል፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ በሀገራችንም ሆነ በአካባቢያችን እየሆነ ያለው ይህ አይደለም፤ አለመግባባት በዝቶአል፣ ማኵረፍና መቀያየም ሰፍቶአል፤ ነገሩ ሁሉ ግራ የሚያጋባና የተመሰቃቀለ ሆኖ ይታያል፡፡

ችግሩ ከሕዝብ አልፎ የአምልኮ ስፍራዎችንና የአምልኮው ፈጻሚዎችን ዒላማ ያደረገ እግዚአብሔርን መዳፈር እየተለመደ መጥቶአል፤ ይህ ለአንድ ሀገር ወይም ሕዝብ የውድቀት ምክንያት ከሚሆን በቀር ከቶውኑም የዕድገት ምልክት ሊሆን አይችልም፡፡
ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ ክፉ ድርጊት እየተፈጸመ ያለው በእኛው ልጆች በኢትዮጵያውያን መሆኑ ነው፤ ስለሆነም በከተማም፣ በጫካም፣ በገጠርም በየትኛውም ስፍራ የምትገኙ ልጆቻችን ምንም ይሁን ምን ሀገርንና ሕዝብን ከመጉዳት ተቆጠቡ፡፡ በተለይም ከቤተ ክርስቲያንና ከሀገር እንደዚሁም ሕዝቡን ከሚያገለግሉ ካህናትና ሲቪል ሰራተኞች እባካችሁ እጃችሁን አንሡ፤ ቤተ ክርስቲያን እኮ የእናንተና የሕዝቡ ሁሉ እናት ናት፤ በእናታችሁ ላይ መጨከንን እንዴት ተለማመዳችሁት? አሁንም ንስሐ ግቡ ያለፈው ይበቃል፡፡ ልብ በሉ ከእግዚአብሔር ጋር መጣላት አይበጅም፤ ሰውን መጉዳትና እግዚአብሔርን መዳፈር አቁሙ፤ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሥርዓተ አምልኮም ያለቦታው አታውሉ፤ ጥያቄአችሁን በሰላማዊ መንገድ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

17 Oct, 09:20


#በከመዝ_ነአምን_ምሥጢረ_ሥላሴ

“አብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ ወልድም ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ መንፈስ ቅዱስም ከአብ ከወልድ ተለይቶ የኖረበት ዘመን የለም፤ ሥሉስ ቅዱስ በዘመኑ በቀኑ ሁሉ በግብርም በስምም ሳይለወጥ ሳይፋለስ ጸንቶ ያለ ነው እንጂ።

ጥንት የሌለው ቀዳማዊ ልጅ ያለው እግዚአብሔር አብ ብቻ ነው ።ዳግመኛ እርሱ ወልድም አይመረመርም ማንም መርምሮ አያገኘውም።

አብ ከዘመን በኋላ አልወለደውም እርሱ ቀዳማዊ ወልድ ከአብ ጋር በቅድምና የነበረ ነው:: እንጂ የማይሞት ከአብ ጋር ፈጣሪ ነው፤ እንደ አብም ሁሉን የፈጠረ ነው።

እንዲሁ መንፈስ ቅድርስም ከአብ ከወልድጋር በቅድምና የነበረ ቀዳማዊ ነው፤ በሥራውም ሁሉ ከአብ ከወልድ ጋር አንድ ነው።

ጉባኤ የቆመላት ቤተክርስቲያን የተቀበለችው ሐዋርያት ያስተማሩት እውነኛ ትምህርት ይህ ነው።

አምነውበት ጸንተውበት ይኖሩ ዘንድ የተነገረው ነገር ሁሉ በየክፍሉ ያለው ምክንያቱ ምን እንደሆነ ዘንድ ላልተማሩት ዕውቀት እንድትሆን አባቶቻችን በኒቂያ የወሰኗት የደነገጏት የከበረች ሃይማኖት ይህች ናት:: “

#ሃይማኖተ_አበዉ
#የቅድስት_ሥላሴ_በረከት_አይለየን!

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

15 Oct, 01:50


#ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_ለኢትዮጰያ_ሕዝብ_ምሕረትን_የለመነ

#ጥቅምት_5 ቀን በምድረ በዳ እንደ መላእክት የኖሩትና በዝቋላ ተራራ ባለው ባሕር ውስጥ 100 ዓመት ተዘቅዝቀው ለኢትዮጵያ ሰዎች ምሕረትን የለመኑት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቃል ኪዳን የተቀበሉበት ዕለት በሀገራችን ኢትዮጵያ በድምቀት ይከበራል፡፡

የማይሰለች ተጋዳይ የክብር ኮከብ የገዳም መብራት ስም አጠራሩ እርግናው የተመሰገነ ብጹእ ቅዱስ ደግ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከግብጽ ደቡብ ከቆላው አገር ከንሂሳ የተገኘ ገዳማዊ አባት።

በግብጽ በረሃ 300 ዓመት የኖረ ከዚያም ወደ ኢትዮጵያ ወጥቶ በዝቋላ ገዳም እህል ሳይበላ ውኀ ሳይጠጣ ልብስ ሳይለብስ 262 ዓመት የኖረ ኑሮውም እንደ ሰው ያልነበረ በምድር ላይ እንደ መላእክት ሆኖ የኖረ፤

የሃይማኖር አርበኛ ገድሉ ትሩፋቱ ከሰማይ ከዋክብት ከምድር አሸዋ የበዛ ኢትዮጰያን አብዝቶ የሚወዳት « አቤቱ ጌታ ሆይ የኢትዮጰያን ሕዝብ ማርልኝ» ብሎ ፈጣሪውን የለመነ ምድራዊ ምግብ ያልተመገበ፤

የእናቱን ጡት እንኳን ያልጠባ ልብስ መጠለያ እንኳን ያልፈለገ የክረምት ቁር የበጋ ሐሩር እየተፈራረቀበት በተጋድሎ 562 ዓመት የኖረ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ።

#የአቡነ_ገብረ_መንፈስ_ቅዱስ_ረድኤት_በረከታቸው_ይደርብን_በጸሎታቸው_ይማረን !

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

13 Oct, 01:03


አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ pinned «የ፳፻፲፮ ዐ.ም የጽጌ የሁለተኛ ሳምንት ምንባባት 🌼የገባሬ ሰናይ (የ አንደኛዉ) ዲያቆን🌼 🌹🌹🌹🌹🌹ኤፌ፡ 6፥1-10🌹🌹🌹🌹🌹 ¹ ልጆች ሆይ፥ ለወላጆቻችሁ በጌታ ታዘዙ፥ ይህ የሚገባ ነውና። ²-³ መልካም እንዲሆንልህ ዕድሜህም በምድር ላይ እንዲረዝም አባትህንና እናትህን አክብር፤ እርስዋም የተስፋ ቃል ያላት ፊተኛይቱ ትእዛዝ ናት። ⁴ እናንተም አባቶች ሆይ፥ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው…»

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

13 Oct, 01:03


አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ pinned «ምስባክ ዘካልዓይ ጽጌ ሰንበተ ክርስቲያን 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 ኤፌ ፮÷፩-፲ ራእ ዮሐ ፲፪÷፩-፲፫ ግብ ሐዋ ፮÷፳፫-፴ ወንጌል፦ሉቃ ፲፪÷፲፮-፴፪ ቅዳሴ፦ዘእግዝእትነ ምስባክ፦ ተዘከር እግዚኦ ከመ መሬት ንሕነ፤ ሰብእሰ ከመ ሣዕር መዋዕሊሁ፤ ወከመ ጽጌ ገዳም ከማሁ ይፈሪ። ትርጉም፦ አቤቱ እኛ አፈር እንደሆን አስብ፤ ሰውስ ዘመኑ እንደሣር ነው፤ እንደዱር አበባ እንዲሁ ያብባል። መዝ ፻፪÷፲፬»

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

12 Oct, 10:16


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የሁለተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

12 Oct, 10:16


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የሁለተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

12 Oct, 10:16


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የሁለተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

12 Oct, 10:16


፩ኛ ዓመት ፩ኛ ዙር የጽጌ ማኅሌት የሁለተኛ ሳምንት ወረብ

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

09 Oct, 09:26


#በመንግሥተ_ሰማያትም_የክብር_አክሊልን_ተቀበለች

#መስከረም_29_ቀን ቅድስት አርሴማ በሰማዕትነት ያረፈችበት ዓመታዊ በዓለ ንግሷ ነው እንዲት ቢሉ ንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ ቆንጆ ሴት ፈልጋችሁ ስዕሏን ስላችሁ አምጡልኝ ብሉ ሠራዊቱን በየሀገሩ በሰደደ ጊዜ ቅድስት አርሴማ ከ 71 ደናግል ጋር ከተራራ ወጥታ ተቀምጣ ነበር፡፡

እየፈለጉ ሲሄዱ የንጉሱ ባለሟሎች ቅድስት አርሴማን አይተው ስዕሏን ስለው ወስደው ሰጡት መልካም ብላቴና አግኝታችሁልኛል ሄዳችሁ አምጡልኝ አላቸው ።

እሷም በንጉሡ መፈለጓን በመንፈስ ተረድታ አርማንያ ወደ ሚባል ሀገር ወረደች ይህን ሰምቶ በወቅቱ ለነበረው ሀገረ ገዢ ለንገሡ ድርጣድስ አስፈልገህ ላክልኝ ብሎ መልእክተኛ ላከበት ፡፡

ቅድስት አርሴማን የአርማንያ ንጉሡ አስፈልጎ ባገኛት ጊዜ እሱም መልከ ቀናነቷን አይቶ ይህችንስ አሳልፌ አልሰጥም ብሎ ወሰዳት መልኳን አይቶ በስሜት ተሸንፎ ዘሎ ያዛት ።

ኃይል መንፈሳዊ ተሰጥቷታልና ጎትታ ከመሬት ጣለችው ንጉሥ ነውና ቢያፍር በሰይፍ አስመታት ከዚህም አያይዞ ከቅድስት አርሴማ ጋር የነበሩትን ሰባ አንዱንም ደናግል ሁሉ በሰይፍ አስመትቷቸዋል ፡፡

ከብዙ ተጋድሎ በኋላም ቅድስት አርሴማም ቃል ኪዳንን ተቀበለች ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋራ ወርዶ « ቅድስት አርሴማ ሆይ ሰላምታ ይገባሻል ስለኔ ፍቅር ይህንን ዓለምና ከሀዲውን ንጉሥ ድል ነስተሽዋልና ምን አደርግልሽ ዘንድ ትወጃለሽ ? » አላት ።

ቅድስት አርሴማም « መታሰቢያየን ያደረገውን ፤ ስሜን የጠራውን ፤ ቤተ ክርስቲያን በስሜ ያሰራውን ፤ ሁሉ መልካም ዋጋውን ክፈልልኝ » አለችው ጌታም « ይህንን ሁሉ ያደረገውን በመንግሥተ ሰማያት ዋጋውን እከፍለዋለሁ» ብሎ ቃል ኪዳኑን አጸናላት ።

#ከቅድስት_አርሴማ_ረድኤት_በረከትን_አምላከ_ቅዱሳን_ያድለን!

#ይኽ_ትምህርት_ለሁሉም_የተዳረሰ_ይሆን_ዘንድ_ሼር_ላይክ_ኮመንት_እናድርገዉ_ቻናሉንም_ለብዙዎች_ተደራሽ_እያደረግን_የሚሰጡ_ትምህርቶችን_በማዳረስ_ሐዋርያዊ_አገልግሎት_እንስጥ!

አምኀ ተዋሕዶ ዘክርስቶስ በYoutube

Sador Sisay on Youtube

Sador Sisay on Instagram

Sador Sisay on Facebook

Sador Sisay on Tiktok

#You_tube #Instagram #Facebook_pages subscribe እና share እያደረጋችሁ አገልግሎታችንን ተደራሽ በማድረግ አግዙ🙏🙏🙏

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

08 Oct, 06:06


#ቅዱስ_ዐማኑኤል

ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረ፣ ያበጃጀ፣ የመሠረተ፤ ያሳመረም እርሱ ነው። ለዐፈር ሕይወትን የሰጠ መሬትም የዘሩባትን ታበቅል ዘንድ ዕፅዋትንም ታስገኝ ዘንድ ሕዋስን የሰጣት እርሱ ነው፡፡ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ይንቀሳቀስ ዘንድ አካልን የሰጠ እርሱ ነው። ሁሉም ፍጥረታት በተሰጣቸው ቦታ ውስጥ ይኖሩ ዘንድ ለሁሉም የፍጥረታት ዘሮች ቦታ ከፍሎ የሰጣቸው እርሱ ነው፡፡

ፍጥረታት ሁሉ የራሳቸው መልክ ይኖራቸው ዘንድ መለያ ቍጥር ሳያደርግባቸው የሁሉንም ፊት የተለያየ እንዲሆን ያደረገ እርሱ ነው፡፡ የሁሉንም ዘሮች ኅሊና ያደሰ እርሱ ነው። ጥበብን ሁሉ የዘራ እርሱ ነው። ሰማያትን የዘረጋ፣ በብርሃናትም ያስጌጣቸው እርሱ ነው፡፡ ለፍጥረታት ሁሉ ስም የሰጠ ምድርም ሊደረስበት የማይቻል ምንጭ ታመነጭ ዘንድ የሰጣት እርሱ ነው።

ተራሮችን የቀረጸ ከፍታዎችንም የሠራ እርሱ ነው። ሣሮችን የሚያዝዝ፣ ዛፎች እንዲበቅሉ፣ ፍሬም እንዲያፈሩ የሚያደርግ፣ እንዲበስሉም ፍሬዎችም እንዲያድጉ የሚያደርግ እርሱ ነው። የፍሬዎች ጣዕም እንዲለያይ የሚያደርግ ለአበቦችም መልክ እና ቅርፅ የሚሰጥ እርሱ ነው።

ሰማያትን በእጆቹ የሚለካ በኃይሉ ሁሉን የሚለካ ሲሆን እርሱ ግን የማይለካ እርሱ የማይወሰን ሲሆን የመሬትን ዐፈር አንዳች ሳትጎድል በእጆቹ የሚገድብ የሚለካም እርሱ ነው።

ሊደረስበት በማይቻል ዕውቀት የተራሮችን ክብደታቸውን የከፍታዎችንም ሚዛን የሚያውቅ እርሱ ነው፡፡ የባሕርን ውኃዎች አንድ ላይ የሰበሰበ በባሕር ጥልቀት ውስጥ ያሉትን ፍጥረታት ሁሉ እያንዳንዳቸውን የሚያውቅ እኛ ልንለካው የማንችለው የባሕር ውኃ በእርሱ ፊት ግን እንደ ጠብታ የሆነ ነው፡፡

#ቅዱስ_ኤፍሬም_ሶርያዊ

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

08 Oct, 05:52


አቤቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ቁርጥ ልመናችንን ስማን፡፡ድዳ ለነበሩት ቃል፡ ለተሰበሩት ምርኩዝ፡ ለእውራን ብርሃን፡ ለአንካሶች መሄጃ፡ ለምጻሞችን የምታነፃ ሆንካቸው፡፡ በደዌ የተያዙትን አቤቱ አዳንህ፡፡ ደንቆሮዎችን ፈወስህ፡፡

ሞትን ዘለፍከው፡፡ ጨለማን አስወገድከው፡፡ ብርሃንን የፈጠርክ ሕልፈት የሌለብህ ፀሐይ፡ የማትጠፋ ፋኖስ፡ በቅዱሳን ላይ ዘወትር የምታበራ ፀሐይ፡ በተወሰነ በቁርጥ ፈቃድ ለዓለም ጌጥ ሁሉን የፈጠርክ ሆይ ቁርጥ ልመናችንን ስማን፡፡

ሰውን ለማዳን ለሁሉ ተገለፅህ፡፡ ነፍስን የመለስካት አንተ ነህ፡፡ ሁሉን እንደሚገባ ማሰብን አስቀደምህ፡፡ መላእክትን የፈጠርህ፡ የሁሉ አባት፡ የሁሉ ጌታ፡ የዓለም ጌጥ፡ ምድርን የፈጠርካት አንተ ነህ፡፡ እንደ ፈቃድህ የሆነውን ልመና ስማን፡፡

ዓለም ሳይፈጠር የነበርህ ጥበብና እውቀት፡ ከአብ ወደዚህ ዓለም ተላክህ፡ ይህ አኗኗር የማይለወጥ፡ የማይፈርስ፡ የማይመረመር ነው፡፡ የማይታይ መንፈስ ነው፡፡ ይህን የተናገርህ አንተ ምስጉን ነህ፡፡ ስምህም፡ ምስክርነትህም የተደነቀ ነው፡፡ ስለዚህ እኛ አገልጋዮችህ እናመሰግንሃለን፡፡

ጸሎተ ኪዳን

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

06 Oct, 11:05


Channel photo updated

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Oct, 14:37


#በአበባው_ቁጥር_ልክ_ሃምሳ_ሃምሳ_ጊዜ

በ15 ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአባ ዜና ማርቆስ አስተማሪነት ከአይሁዳዊነት ወደ ክርስቲያንነት የተመለሰው አባ ጽጌ ብርሃንና ( ጽጌ ድንግል ) አባ ገብረ ማርያም መምህር ዘደብረ ሐንታው ሁለቱ ማኅሌተ ጽጌንና ሰቆቃወ ድንግልን ድርሰት ደርሰው የእመቤታችንን ስደቷን እያሰቡ ማኅሌት መቆም ጀመሩ።

ለማመን ያበቃቸውም ገባሪተ ኃይል የሆነች የእመቤታችን ሥዕል ነበረች። ብዙ ተዓምራትን ስታደርግ ስላየ ወደ አባ ዜና ማርቆስ በመሄድ ተምሮ ለማመን በቃ በምንኩስና ሕይወት መኖር ከጀመረ በኋላም ያቺ ለማመን ያበቃችውን ገባሪተ ኃይል ሥዕል ሳይሳለም አይውልም ነበር።

ከሥዕሏ ፊትም ሲቆም የሚያቀርበው እጅ መንሻ ( መባዕ ) ስለሌለው ይጨነቅ ነበር በኋላ ግን ይህ ዘመነ ጽጌ ሲደርስ በየቀኑ ሃምሳ ሃምሳ የጽጌረዳ ዘለላ አበባ እየፈለገ እንደ ዘውድ እየጎነጎነ ለዚያች ምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል ያቀዳጃት ነበር።

የበጋው ወቅት ሲመጣ አበባው ስለሚደርቅበት ከሥዕሏ ተንበርክኮ ስለ አበባው ፈንታ መልአኩ ተፈሥሒ ተፈሥሒ እያለ ያመሰገነሽን ምስጋና በአበባው ቁጥር ልክ ሃምሳ ሃምሳ ጊዜ እንዳመሰግንሽ ፍቀጂልኝ በማለት ተማጽኖ በየቀኑ ምስጋናው እንደ ጽጌረዳ አበባ እየሆነ ከአንደበቱ ሲወጣ እመቤታችን አበባውን እየተቀበለች ስትታቀፈው ሰዎች እያዩ ያደንቁ ነበር ።

« ማርያም ሥዕልሽ በዓለም እንዲህ የምታበራ ከሆነ በሰማይ የፊትሽ መልክ ምን ያምር ! አንቺን ከማየት የሚገኘውን ደስታ እጠግብ ዘንድ በሕልም ተገለጪልኝ ዝናብ ሊያጠፋው የማይቻለው የፍቅርሽ እሳት አንድዶኛልና »

#አባ_ጽጌ_ድንግል
#የአባቶቻችን_የአባ_ጽጌ_ድንግል እና #የአባ_ገብረ_ማርያም_በረከታቸዉ_ይደርብን!

#አምኀ_ተዋኅዶ_ዘክርስቶስ
https://t.me/Ameha_Tewahdo_Zcristos

አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ

05 Oct, 13:52


አምኀ ተዋኅዶ ዘክርስቶስ pinned «🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 የ፳፻፲፮ ዐ.ም የጽጌ የመጀመርያ ሳምንት ምንባባት 🌼የገባሬ ሰናይ (የ አንደኛዉ) ዲያቆን🌼 🌹🌹🌹🌹🌹ሮሜ፡ 5፥20-21🌹🌹🌹🌹🌹 20 “በደልም እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ፤ ዳሩ ግን ኃጢአት በበዛበት፥ ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ፥ 21 እንዲሁ ደግሞ ጸጋ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣ በጽድቅ ምክንያት ለዘላለም ሕይወት ይነግሥ ዘንድ፥ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በለጠ።” 🌼የንፍቁ…»

12,196

subscribers

1,477

photos

15

videos