AHADU RADIO FM 94.3 @ahaduradio Channel on Telegram

AHADU RADIO FM 94.3

@ahaduradio


አሐዱ ራድዮ 94.3
Your source for top local and international news and analysis.
"Voice of Ethiopian"
የአሐዱ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን ወቅታዊና እውነተኛ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ

AHADU RADIO FM 94.3 (Amharic)

አሐዱ ራድዮ 94.3
በእርሱ አትቀመጡ፦ 'AHADU RADIO FM 94.3' የቴሌግራምና የቴሌቧል ኢትዮጵያ መረጃዎች እና ምንም እንደሆነ ከአንድ እስር ቤተሰብ የሚገኝበት ሕይወት ሲሆን ኢትዮጵያዊን እና ለዓለም ሳሆማ ወቅቶችን ለመጫወት በመቀየት እንጠናቅቃለን። ከአንዱን እስር እስከ ሌሎችን መረጃዎች ዘገቦች በዚህ ቤተሰብ በዓል አድርገን የእንቆማ የቅድመ-ምርምር እና ፕሮግራሞችን ልክቶለን። ከሌሎች ቦታዎች ውስጥ በጣም ካሉት መጽሐፍ እንጠብቃለን እና ማጠናቀቅን ስለሚችል ከዚህ የሚቆይ አንዱን ስኬት አስተናግዶ ቀበሌ፣ እጠቀማለን።

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 17:10


#አሐዱ_አብይ_ጉዳይ

"ጥርስ አልባው አንበሳ የአፍሪካ ህብረት" 

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/h7c7Trk5Ndc?si=KLe2PNGQsR_G976Q

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 15:43


የጅቡቲው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማሕሙድ የሱፍ አዲሱ የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሆነው ተመረጡ

የካቲት 8/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የጅቡቲ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማሕሙድ አሊ የሱፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል።

ማሕሙድ አሊ የሱፍ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር እንዲሆኑ 33 ድምጽ በማግኘት ማሸነፋቸው ነው የተነገረው።

የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ ለኮሚሽነርነት የተመረጡት የኬንያው የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እና የማዳጋስካር የቀድሞ የኤኮኖሚ እና የፋይናንስ ሚኒስትር ሪቻርድ ራንድሪያ ማንድራቶን በማሸነፍ ነው።

በዚህም መሠረት ላለፉት ስምንት ዓመታት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የነበሩትን ሙሳ ፋኪ ማኅማትን የተኩት የ59 ዓመቱ ማሕሙድ አሊ ይሱፍ፤ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን የሚመሩ ይሆናል።

በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ በመካሄድ ላይ በሚገኘው 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ መክፈቻ ላይ፤ የሕብረቱ ሊቀመንበር የነበሩት የሞሪታኒያው ፕሬዝዳንት ሞሃምድ ኡልድ ጋዝዋኒ የሕብረቱ ሊቀ-መንበር ሆነው ለተመረጡት የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዧ ማኑኤል ጎሳዌስ ሎሬንሶ ሊቀመንበርነቱን ማስረከባቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 15:11


"አፍሪካ በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባል እንድትሆን እንሰራለን" አንቶንዮ ጉተሬዝ

👉 "በአፍሪካ ሰላምን እና ደህንነትን ለማረጋገጥ አለም አቀፉ ማህበረሰብ በትብብር ሊሰራበት የሚገባ አጀንዳ ነው" ብለዋል


የካቲት 8/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አፍሪካ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት የምትፈልገውን ውክልና እንድታገኝ እንሰራለን ሲሉ፤ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሀፊ አንቶንዮ ጉተሬዝ ገለጹ።

ዋና ጸሀፊው 38ኛው የአፍሪካ ሕብረት መደበኛ የመሪዎች ጉባኤ መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ "የተመድና የአፍሪካ ሕብረት ግንኙነትን ሊጠናር ይገባል" ብለዋል፡፡

"ተመድ በማንኛውም ሁኔታዎች ከአፍሪካ ሕብረት ጋር ያለውን ግንኙት ለማጠናከር በሩ ክፍት ነው" ሲሉም ተናግረዋል፡፡

አፍሪካ እስካሁን ድረስ በተመድ የጸጥታው  ምክር ቤት ውስጥ ቋሚ ተወካይ የሌላት መሆኑን ገልጸው፤ "ከአፍሪካ ሕብረትና አባል ሀገራት ጋር በመሆን አፍሪካ የምትፈልገውን ውክልና እንዲታገኝ እንሰራለን" ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በጸጥታው ምክር ቤት ሁለት ቋሚ የጸጥታው ምክር ቤት አባል እንዲኖራት እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

"አፍሪካ ከዓለም አቀፍ የፋይናንስ ድርጅቶች ፍትሃዊ እና አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲታገኝ ጥረት ይደረጋል" ሲሉም አስረድተዋል፡፡

"የዘንድሮው ጉባኤ አፍሪካ በቅኝ ግዛት የደረሰባትን ጫና መከስ እንዳለባት ለሌላው ዓለም የምታንጸባርቅበት ነው" ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል አፍሪካ ካላት የሕዝብ ብዛት ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዘው ወጣቱ በመሆኑ፤ ያላትን የሰው ኃይል በአግባቡ ልትጠቀምበት እንደሚገባ አስታውቀዋል፡፡

በተጨማሪም ጠዋት በተካሄደው በሕብረቱ መደበኛ ስብሰባ መክፈቻ ላይ የተሳተፉ አንቶንዮ ጉተሬዝ  ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ "በአፍሪካ ሰላምን እና ደህንነትን ለማረጋገጥ አለም አቀፉ ማህበረሰብ በትብብር ሊሰራበት የሚገባ አጀንዳ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

"አፍሪካ በአሁን ወቅት ለየት ያሉ ችግሮች እያጋጠሟት ነው" ያሉም ሲሆን፤ ሥር የሰደደው ቀኝ ግዛት፣ የባሪያ ንግድና ሌሎችም ኢ-ፍትሐዊ አሰራሮች በአፍሪካ ላይ ጠባሳ ጥሎ ማለፋቸውን ተናግረዋል።

አፍሪካ በተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ አባልነት እንድታገኝ ጥረት እንደሚደረግም አንስተዋል።

"የዓለም አቀፉ የኢኮኖሚና ፋይናንስ መዋቅር አፍሪካን ያማከለ አይደለም። ኢ-ፍትሐዊ አሰራሮችን ማስተካከል ለሚስተዋሉ ችግሮች መፍትሔ የሚያሰጥ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

የአሁኑ ውይይት በአራት ጉዳዮች ላይ እንደሚያጠነጥ ያነሱት ዋና ጸሀፊው፤ ልማትን በማፋጠን ዘላቂ የልማት ግቦችን ለሳካት ዓለም አቀፉ የፋይናንስ መዋቅር አፍሪካን በማከለ መልኩ ሪፎርም እንዲያደርጉ ግፊት ማድረግ የመጀመሪያው መሆኑን ገልጸዋል።

ሌላው ፍትህን በማረጋገጥ በአፍሪካ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ላይ ምዕራባዊያን ያላቸውን አሉታዊ አተያይ መቀየር መሆኑን አንስተዋል።

በተጨማሪም በቴክኖሎጂና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፍ የአፍሪካውያንን ተጠቃሚነት ማጎልበት እና በመላው አፍሪካ ሰላምና ደህንነትን ማረጋገጥ ላይ እንደሆነ ጠቁመዋል።

በትላንትናው ዕለት በኮንጎ ሪፐብሊክና በሱዳን ከሚስተዋለው ግጭት ጋር ተያይዞ በአፍሪካ ሕብረት የሰላም ደህንነት ምክር ቤት ጉባኤ ላይ መሳተፋቸውን ጠቁመዋል።

"በሱዳን ካለፉት ሁለት ዓመታት ጊዜ ጀምሮ ባለው ግጭት የንፁሃን ግድያ፣ የጾታዊ ጥቃትና የሰብዓዊ መብት ጥሰት እየተስተዋለ ነው" ያሉት አንቶንዮ ጉተሬዝ፤ ይህም ለቀጠናው ስጋት መሆኑን መናገራቸውን ኢፕድ ዘግቧል።

አክለውም "ለግጭቶች ምንም አይነት ወታደራዊ መፍትሔ የለም ያለንበት ጊዜ የመሳሪያን ድምፅ የሚወገድበት የዲፕሎማሲና የውይይት ነው" ብለዋል።

መግለጫቸውን ሲያጠናቅቁም በሁሉም ሁኔታዎች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ከአፍሪካውያን ጋር መሆኑን አስገንዝበዋል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 13:28


ኢትዮጵያ በቢዝነስ ቱሪዝም ከ1 ሚሊዮን በላይ ጎብኚዎችን ታስተናግዳለች ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለጸ

የካቲት 8/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በያዝነው ዓመት ኢትዮጵያ የቢዝነስ ቱሪዝምን በመጠቀም ከአንድ ሚሊዮን በላይ ጎብኚዎችን በመቀበል ታስተናግዳለች ተብሎ እንደሚጠበቅ የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል።

ይህም በኢትዮጵያ የመጀመሪያው እንደሚሆን ነው የተገለጸው፡፡

እስካሁን ድረስ ባለው አሰራር መሰረት ምን ያክል ቱሪስት ወደሀገር ውስጥ ገባ? ምን ያክሉስ የሀገር ውስጥና የውጪ ነው? እንዲሁም ምን ያክል ቀን አሳለፈ? የሚሉትን መረጃዎች ለማወቅ ከኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት በሚያገኘው ዳታ ተመስርቶ እንደሚሰራ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የኢትዮጵያ ኮንቬንሽን ቢሮ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ጌትነት ይግዛው ለአሐዱ ገልጸዋል።

"በመሆኑም በ2016 በጀት ዓመት በተመረቀው የቱሪዝም ሳተላይት አካውንት አማካኝነት፤ በዚህ ዓመት የነበሩ ክፍተቶችን በመሙላት እና የቱሪስትን ሙሉ መረጃ በማጠናቀር በቅርብ ጊዜ ከ1 ሚሊዮን በላይ ቱሪስት እናስተናግዳለን" ሲሉ ተናግረዋል።

ዘመናዊ የኢትዮጵያ ቱሪዝም ከ60 ዓመት በላይ ቢያስቆጥርም ይህንን ያህል ቁጥር ያለው የውጭ ሀገር ጎብኚ እንዳላስተናገደ የገለጹት መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ የያዝነው ዓመት የተሻለ አፈፃፀም ይኖራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

ለዚህም እንደዋና ምክንያት ያነሱት ሀገሪቱ አንድ ትልቅ የቱሪስት ቡድን ተብሎ ከ21 እስከ 25 ሰው ከሚሳተፍበት የባህላዊ፣ ተፈጥሯዊና ታሪካዊ ቱሪዝም ይልቅ፤ በአንድ ጊዜ ከ1 ሺሕ 500 እስከ 2000 የጉባዔ ተሳታፊዎችን በሚያካትተው ወደ "ቢዝነስና ሌዠሪ ቱሪዝም ዘርፍ መሸጋገሯ እንደሆነ አስታውቀዋል።

በ2017 በጀት ዓመት በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ53 በላይ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎች መከናወናቸውን በመጥቀስ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ 22 ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እያንዳንዳቸው በፈረንጆቹ 2025 እስከ 2027 ዓ.ም. በትንሹ 6 ዓለም አቀፍ ጉባኤዎችን እንደሚያካሂዱ ገልጸዋል።

በአጠቃላይም በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ ከ300 እስከ 400 የሚጠጋ የዓለም አቀፍ ጉባዔ በአዲስ አበባ ይስተናገዳል ተብሎ እንደሚጠበቅም አመላክተዋል።

አዲስ አበባ ለቢዝነስ ቱሪዝም እንደዋና መናኸሪያ ትሁን እንጂ፤ በቀጣይ የክልል ዋና ዋና ከተሞችን በማነቃቃት ወደ ቢዝነስ ቱሪዝም እንዲመጡ የማድረግ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም መሪ ሥራ አስፈፃሚው ለአሐዱ ተናግረዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!

ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 12:36


"የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ለኢትዮጵያ ያበረከቱት አስተዋፅኦ በቀላሉ ተነግሮ የሚታለፍ አይደለም" የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ

የካቲት 8/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የማስተማሪያ ሆስፒታል ለኢትዮጵያ የጤና ሥርዓት መሻሻል ያበረከቱት አስተዋፅኦ በቀላሉ ተነግሮ የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም ሲሉ የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ ተናግረዋል፡፡

ሚኒስትር ዴዓታው ይህን ያሉት በዛሬው ዕለት በተከናወነው የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ነው፡፡

በመልዕክታቸውም የዩንቨርስቲውን አስተዋፅኦ ሲያብራሩ፤ "በርካቶቻችን ከዚህ ዩኒቨርስቲ በወጡ መምህራን ተምረናል፣ በርካቶቻችን በዚሁ ዩንቨርስቲ ተምረናል፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በዚሁ ዩንቨርስቲ ታክመዋል፣ ድነዋል በርካታ ዜጎቻችን ለዚህ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ቀስመው ወጥተዋል" ብለዋል፡፡

በተጨማሪም በርካታ ምርምሮች በዩንቨርስቲው መደረጋቸውን በማንሳት፤ ለኢትዮጵያም ሆነ ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጠቃሚ የሆኑ እጅግ ብዙ የማህበረሰብ አገልግሎቶችና ዩኒቨርስቲውንና ማኅበረሰቡን ያገናኙ ሰፊ የልማት ሥራዎች በዩንቨርስቲው ስለመሰራታቸው ተናግረዋል፡፡

"ትምህርት ለሁሉም ነገር መሠረት ነው" ያሉት ሚንስትር ዴዔታው፤ ያለ ትምህርት ያደገ የትኛውም አገር የለም፡፡ የዓለም ታሪክ እንደሚያስረዳው አገራት የበለፀጉት እና ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሱት በትምህርት ላይ በሰሩት ሥራ ባመጡት ለውጥ ነው" ብለዋል፡፡

በዚህም ምክንያት መንግሥት ለትምህርት ጥራት ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት፤ ለበርካታ ዘመን የነበረውን የትምህርት ስብራት በመጠገን በአጠቃላይ ትምህርት እንዲሁም በከፍተኛ ትምህርት ላይ በርካታ የሪፎርም ሥራዎችን እየተገበረ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በተለይ የመውጫ ፈተና በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲሰጥ በመወሰኑ፤ ባለፉት ሁለት እና ሦስት ዓመታት የተገኙ መሻሻሎች የሚያበረታቱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

አክለውም "ዘንድሮ በዩንቨርስቲ የመውጫ ፈተና ከፍተኛ ውጤትን በማስመዝገብ፤ የዩኒቨርስቲውን ሥም ያስጠራችሁ ተማሪዎች መምህራንና አጠቃላይ የዩኒቨርስቲ ማህበረሰብ በየመውጫ ፈተና ላይ ከፍተኛ ለውጥ ስላመጣችሁ እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል፡፡

"የሕክምና ደመወዝ የማኅበረሰቡ ከበሽታ መዳን እና ጤናማ መሆን ነው፡፡ የሐኪም ደመወዝ ማኅበረሰቡ የሚያገኘው ደስታ እና እርካታ ነው" ያሉት ዶ/ር ደረጄ፤ "ምንም ያክል ቢከፈል ለሐኪሞቻችንና ለጤና ባለሙያዎቻችን በቂ አይደለም" ሲሉም ተናግረዋል፡፡

የሕክምና ትምህርት አድካሚ የሆነበት ምክንያት በቀጥታ ከሰው ሕይወት ጋር የተገናኘ ከመሆኑም ባሻገር፤ በአጠቃላይ በሀገራችን ለሚፈልገው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥ እጅግ ጠቃሚ በመሆኑን ነው ሲሉም አብራርተዋል፡፡

"ይህ ከመሆኑም የተነሳ ይህንን ከባድ ተልዕኮ በአግባቡ ወስዳችሁ ባለፉት በርካታ ዓመታት ትምህርታቸውን በትጋት የጨረሳችሁ ተመራቂ ተማሪዎች፤ ቀጣዩ የሕይወታቸው ምዕራፍ ቀላል ላይሆን ይችላል" ብለዋል፡፡

ይህንንም ሲያብራሩ "ተመራቂዎች ከራሳቸው በላይ ለማህበረሰባችሁ፣ ለሕዝባችሁና ለሀገራቸውና የምታስቡበት፤ ኃላፊነትን የበለጠ የምትለማመዱበትና ኃላፊነትን የምትሸከሙበት እንዲሁም ያገኛችሁትን ዕውቀት እና ክህሎት መነሳችሁ ለማህበረሰባቸሁ የምትሰጡበት በመሆኑ ነው" ብለዋል፡፡

በዚህም ምክንያት "ተመራቂ ተማሪዎች ቀጣይ ሕይወታችሁ የትኛውንም ተግዳሮት ለመጋፈጥና የትኛውንም ውጣ ውረዶችን ለመቀበል መዘጋጀት አስፈላጊ ይሆናል" ሲሉ አሳስበዋል፡፡

"ተመራቂዎች ከሌሎች የጤና ሙያተኞችና ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን አካባቢያችሁን እንድትቀይሩ፣ ኃላፊነትን እንድትወስዱና ችግሮችን ለመፍታት ጥረት እንድታደጉ አደራ ማለት እፈልጋለሁ" ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

በሊዲያ አበበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 12:31


የፌደራል መስሪያ ቤቶችን ጨምሮ 35 የሕጻናት ማቆያዎች መዘጋጀታቸው ተገለጸ

👉 የሰው ኃይል እና የቦታ እጥረት ለማቆያዎቹ መስፋፋት እንደ ክፍተት ተነስቷል


የካቲት 8/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከ200 በላይ የሚሆኑ የልማት ድርጅቶችን ጨምሮ በፌደራል መንግሥት ሥር ከሚገኙ ተቋማት መካከል፤ በ6 ወራት ውስጥ 33ቱ በቢሯቸው ውስጥ የሕጻናት ማቆያ እንዲኖቸው መደረጉ ተነግሯል፡፡

የሴቶች እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር የሕጻናት መብት ጥበቃ መሪ ሥራ አስፋጻሚ ወ/ሮ ዘቢደር ቦጋለ እንደተናሩት፤ ተቋማቸው፡- ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በተቋማት ላይ የሕጻናት ማቆያ እንዲዘጋጅ ኃፊነት ወስዶ ላለፉት 7 ዓመታት እየሰራ ይገኛል፡፡

በዚህም መሰረት ባለፉት ስድስት ወራት ውስት ከ70 በላይ ተቋማት የሕጻናት ማቆያ እንዳዘጋጁ አስታውሰዋል፡፡

የተቋማት ደረጃ ከሚገመገምበት መስፈርቶች መካከል የሕጻናት ማቆያ ተጠቃሽ ስለመሆኑ የተነገሩ ሲሆን፤ "የሰው ኃይል እና የቦታ እጥረት በተቋማት ላይ ለሚዘጋጅ የሕጻናት ማቆያ እንደ ተግዳሮት የሚነሱ ጉዳዮች ናቸው" ብለዋል፡፡

በተቋማት ላይ የሚከናወነው የሕጻናት ማቆያ የሥራ ሂደት እየተሻሻለ እንደሚገኝ በሚኒስቴሩ የሕጻናት መብት ጥበቃ መሪ ሥራ አስፋጻሚ ወ/ሮ ዘቢደር ቦጋለ ተናግረዋል፡፡ አክለውም የማኅበረሰብ ሕጻናት ተቋማት እንዲስፋፋ እየተሰራ ይገኛል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በእሌኒ ግዛቸው
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 10:16


#አሐዱ_መድረክ

"የአፍሪካ ሀገራት ለኢትዮጵያ ምን አደረጉ?"

የቀድሞው ዲፕሎማት አምሳሳደር ጥሩነህ ዜናው ከአሐዱ መድረክ ጋር ያደረጉት ቆይታ (ክፍል አንድ)

ውይይቱን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
https://youtu.be/crGbL9b-wpg?si=B2jQeXsnES_KuHvB

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 10:06


የ2025 የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ-መንበርነትን አንጎላ ተረከበች

የካቲት 8/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአፍሪካ ሕብረት ሊቀ-መንበርነትን በ2024 ስትመራ የነበረችው ሞሪታኒያ ስልጣኑን ለአንጎላ አስረክባለች።

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ በሕብረቱ ዋና መቀመጫ አዲስ አበባ መካሄድ ላይ ይገኛል።

በጉባዔው መክፈቻ ላይ የሕብረቱ ሊቀመንበር የነበሩት የሞሪታኒያው ፕሬዝዳንት ሞሃምድ ኡልድ ጋዝዋኒ ለወቅቱ የሕብረቱ ሊቀ-መንበር ሆነው ለተመረጡት የአንጎላ ፕሬዝዳንት ዧ ማኑኤል ጎሳዌስ ሎሬንሶ ሊቀመንበርነቱን አስረክበዋል።

የሞሪታኒያው ፕሬዝዳንት ለአንጎላው አቻቸው መልካም የሥራ ዘመን ተመኝተዋል።

በዚህም መሰረት አንጎላ የ2025 የአፍሪካ ኅብረት ሊቀ-መንበር በመሆን ሥራዋን የምትጀምር ይሆናል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

15 Feb, 09:03


የጎንደር ዩንቨርስቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ያስተማራቸውን 366 ተማሪዎች አስመረቀ

👉የምርቃት ሥነ-ስርዓቱ የዩኒቨርስቲው 70ኛ ዓመት እና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል አንዱ አካል ነው


የካቲት 8/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፤ የ40ኛው ዙር የሕክምና ተማሪዎች እና 21ኛው ዙር የፋርማሲ ተማሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር በዛሬው ዕለት አካሂዷል፡፡

ዩንቨርስቲው በመጀመሪያ ዲግሪ፣ በሁለተኛ ዲግሪ በሦስተኛ ዲግሪ፣ በስፔሻሊቲ እና ሰብ ስፔሻሊቲ የትምህርት ዘርፎች፤ በአጠቃላይ 254 ወንድ እና 112 ሴት በድምሩ 366 ዕጩ ምሩቃንን ነው በዛሬው ዕለት ያስመረቀው፡፡

በምርቃት መርሃ ግብሩ ላይ የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ፣ የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይን፣ የጎንደር ከተማ ከንቲባና የዩንቨርስቲው ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ደብሬ የኋላ፣ የሕዝብ ተወካይ ምክር ቤት አባላት፣ የዩንቨርስቲው ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ተመራቂ ተማሪዎች እንዲሁም የተመራቂ ተማሪ ወላጆች ተገኝተዋል፡፡

የዩንቨርስቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር አስራት አጸደወይን በመርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ በቅድመ ምረቃ እና በድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች በኮሌጅ የትምህርት ጉባዔ ተመስክሮና በዩንቨርስቲው ሴኔት ጸድቆ ለዛሬው የምርቃት ቀን መብቃታቸውን ተናግረዋል፡፡

"ተመራቂ ተማሪዎች ኢትዮጵያ እናንተን በጥብቅ ትፈልጋችኋለችና ይህ ደስታ የእናት ሀገራችሁ ጭምር ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ "የሰለጠናችሁበት የተከበረው የሕክምና እና የጤና ሙያዎች ምን ይህል ፈታኝ ግን ፈዋሽ እንደሆነ እንገነዘባለን" ብለዋል፡፡

አክለውም፤ "እንቅልፍ አልባ ለሊቶች፣ ስንፍና እና ድካም የሻረ ትጋት በብዙ ተግዳሮቶች የተፈተነ ግን ያልተሸነፈ ጥንካሬያችሁ ለዛሬው ቀን አብቅቷችኋልና እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ለተመራቂ ተማሪዎች መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዴዔታ ዶ/ር ደረጄ ድጉማ በበኩላቸው፤ "ተመራቂዎች አድካሚውን የትምህርት ጉዞ በስኬት አጠናቃችሁ በጉጉት ስትጠብቁት ለነበረው የምርቃት ቀናችሁ እንኳን አደረሳችሁ" ያሉ ሲሆን፤ "ቀጣይ የሀገራችን ጉዞ ዛሬ የምትመረቁት ተማሪዎች እጅ ላይ የሚወድቅ ነው" ብለዋል፡፡

አክለውም ተመራቂ ተማሪዎች የተጣለባቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው በማሳሰብ፤ ተመራቂ ተማሪዎች በቀጣይ ወደ ሥራ ሲገቡ ሙያቸውን ያለ ስስት የሚሰጡ እንዲሆኑም ጠይቀዋል፡፡

የተማሪዎች የምርቃት ሥነ-ስርዓቱ የተከናወነው፤ የዩኒቨርስቲው 70ኛ ዓመት እና አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል እየተከበረ ባለበት ወቅት መሆኑ ልዩ እንደሚያደርገውም በመድረኩ ተነግሯል፡፡

በመርሃ ግብሩ ላይም በቅርቡ ሕይወቱ ያለፈውና በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽትና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊስት ሃኪምነት የነበረውን ዶ/ር አንዱዓለም ዳኜን በማሰብ የህሊና ጸሎት ተደርጓል፡፡

በሊዲያ አበበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 17:02


#አሐዱ_አንቀፅ

"በስሜትና በጦርነት የተለወጠ ሀገርም ሆነ ትውልድ የለም!"

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/lh9qGQrcrLU?si=kuy772D3dsicPgNx

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 16:38


ኢትዮጵያ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የወደብ ጥያቄዋን እና አቋሟን ግልጽ ማድረግ አለባት ሲሉ ባለሙያዎች ገለጹ

የካቲት 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ እና በ46ኛው የሕብረቱ የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ፤ ኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄዋን እና አቋሟን ግልጽ ማድረግ አለባት ሲሉ አሐዱ ያነጋገራቸው የዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያዎች ገልጸዋል።

በጉባኤው ላይ ኢትዮጵያ ወደብ አማራጭ ውስጥ የማይገባና መሰረታዊ መሆኑን ማንጸባረቅ እንዳለባትም ባለሙያዎቹ አሳስበዋል።

"ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ወደብ አስፈላጊ ነው" ያሉት የቀድሞው ዲፕሎማት ደያሞ ዳሌ፤ "አስተማማኝ የሆነ ወደብ ማግኘቷ የህልውና ጉዳይ መሆኑን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ማሳመን መቻል አለባት" ብለዋል።

እንዲሁም ከኢትዮጵያ ጋር በተለያየ ምክንያት ቅሬታ ውስጥ የገቡ ሀገራት በኢትዮጵያ ድንበር አካባቢ ወታደሮቻቸውን ማስፈር እንደሌለባቸው ኢትዮጵያ አቋማን ማንጸባረቅ እንዳለባት ገልጸዋል።

ሌላው አሐዱ ያነጋገራቸው የዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ባለሙያው ጥላሁን ሊበን በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ የባህር በር እንዲኖራት ለማድረግ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማጠናከርና በሰላማዊ መንገድ ወደብ ማግኘት እንደምትፈልግ አቁሟን ይፋ ማድረግ እንዳለባት አንስተዋል።

በተመሳሳይም "መንግሥት የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም የሚጠበቅበት ኅላፊነት ሊወጣ ይገባል" ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር የደረሰችውን ስምምነት ይበልጥ ለማጠናከርና ወደብ የምታገኝበት መንገድ ለማግኘት የአፍሪካ ህብረት ጉባኤ መልካም አጋጣሚ መሆኑንም ጠቁመዋል።

አክለውም "ኢትዮጵያ በዲፕሎማሲዉ ጠንካራ እና ተሰሚነት ያላት ሀገር ለመሆን፤ በመጀመሪያ የውስጥ ሰላሟን ማረጋገጥ አለባት" ሲሉ አሳስበዋል።

38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ በመጪው የካቲት 8 እና 9 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ 46ኛው የሕብረቱ የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ደግሞ የካቲት 5 እና 6 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ይታወቃል።

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 15:19


በመዲናዋ ከ10 በላይ ሆስፒታሎች በልማት በመፍረሳቸውና ፍቃድ ባለማደሳቸው ምክንያት ወደ ሥራ አልተመለሱም ተባለ

የካቲት 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ በግማሽ ዓመቱ ከ10 በላይ የሚሆኑ ሆስፒታሎች፣ ክሊኒኮችና የጤና ተቋማት በልማት ምክንያት ካሉበት አካባቢ በመነሳታቸው እንዲሁም የፍቃድ ዕድሳት ባለማድረጋቸው ምክንያት፤ ወደ ሥራ አለመመለሳቸውን የከተማ አስተዳደሩ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን ለአሐዱ አስታውቋል፡፡

"በግማሽ ዓመቱ ምን ያህል የጤና ተቋማት ፍቃዳቸውን ዕድሳት አድርገዋል? ከጥራት ልኬት ጋር በተገናኘ የቁጥጥር ሂደቱ ምን ይመስላል?" ሲል አሐዱ ባለስልጣኑን ጠይቋል።

የባለስልጣኑ የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ብቃት ማረጋገጫ ዳይሬክተር ቡድን መሪ ጉሽ አረፋ በሰጡት ምላሽ፤ በከተማዋ ከሚገኙ 182 ተቋማት ውስጥ 172 የሚሆኑት ብቻ የብቃት መለኪያ መስፍርቱን አሟልተው ወደ ሥራ መግባታቸውን ገልጸዋል፡፡

ነገር ግን ከ10 በላይ የሚሆኑት ከልማት ጋር ተያይዞ ተቋማቸው በመፍረሱ፣ መለኪያውን ባለሟሟላታቸው እንዲሁም ከገበያ በመውጣታቸው ምክንያት እድሳት አለማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ዕድሳት ካላደረጉት የጤና ተቋማት መካከል መሟላት ያሉባቸው መስፈርቶችን አሟልተው የሚመለሱ ተቋማት ድጋሚ ልኬት ተደርጎላቸው ወደ ገበያው እንደሚመለሱም ጠቁመዋል።

በዚህም ሳቢያ በአካባቢዉ የሚገኙ ነዋሪዎች ከመሠረታዊ እስከ ከፍተኛ የጤና አገልግሎቶች እንዳያገኙ እንቅፋት ሊፈጠሩ እንደሚችል ገልጸዋል።

ደህንነቱ የተጠበቀ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው የጤና እና ጤና ነክ አገልግሎት ሙያዊ ብቃት እና ሥነ-ምግባር ባላቸው የጤና ባለሙያዎች ህብረተሰቡ እንዲገለገል እየተሰራ መሆኑን አክለዋል።

በተጨማሪም "የጤና ባለሙያዎችን ብቃት በመመዘን፣ በትብብር በመስራት እንዲሁም ደህንነቱና ጥራቱ የተጠበቀ አገልግሎት እንዲሰጥ በማድረግ የህብረተሰቡን ጤና መጠበቅ ላይ በአጽንኦት እየተሰራ ነው" ሲሉ አብራርተዋል፡፡

"ተቋማቱን ወደ አገልግሎት ለመመለስ ከፍተኛ ቅንጅታዊ ርብርብ ይደረጋል" ብለዋል።

ቡድን መሪው አክለውም፤ በዘርፉ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ከሌሎች ጊዜያት በተለየ መልኩ የቁጥጥር ሥራዎችን በማዘመን ችግሮችን ለማስወገድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየተሠራ መሆኑን አመላክተዋል።

በወልደሐዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 14:52


"የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ ነው" የኢትዮጵያ አየር መንገድ

የካቲት 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከሰሞኑ በማህበራዊ ትስስር ገጾች ሲዘዋወር የነበረው የአንዲት ግለሰብ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ መሆኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ ባወጣው መግለጫ አንዲት ግለሰብ በአውሮፕላኑ መወጣጫ ደረጃ ላይ የተለያዩ ዲኮሮችን በማድረግ የተነሳችው ፎቶ ሲዘዋወር መታየቱን ገልጿል፡፡

ግለሰቧ የተነሳችው ለጥገና በቆመ አውሮፕላን ላይ መሆኑን የጠቆመው አየር መንገዱ፤ ድርጊቱ ከተቋሙ እውቅና ውጭ የተደረገ መሆኑን አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ የሙያ አገልግሎት ሥነ-ምግባርን በመጠበቅ ደረጃውን የሚመጥን አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

ይሁን እንጂ ከጉዳዩ ጋር ተያይዞ ተቋሙ ከሙያዊ ሥነ ምግባር ውጪ ገንዘብ በመቀበል ለግለሰቧ ፈቃድ እንደሰጠ በማስመሰል በተሰራጨው መረጃ ማዘኑን አንስቷል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ ምርመራ እያደረገ መሆኑን የገለጸው አየር መንገዱ÷ ድርጊቱን በፈፀሙ አካላት ላይ አስተዳደራዊ ርምጃ እንደሚወስድ አረጋግጧል፡፡

ከሰሞኑ አንዲት ግለሰብ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አርማን የያዘ አውሮፕላን መወጣጫ ደረጃ ላይ የተለያዩ ዲኮሮችን በማድረግ፤ የተለያዩ የልደት ፎቶዎችን እና ተንቀሳቃሽ ምስሎችን መልቀቀቋን ተከትሎ፤ ጉዳዩ በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኖ ቆይቷል፡፡

አየር መንገዱ ይህን አስመልክቶ ዛሬ ባወጣው መግለጫው፤ " ድርጊቱ ከእኔ እውቅና ውጪ ነው" ይበል እንጂ፤ እንዴት ይህ ድርጊት እንደተፈጸመና ድርጊቱ ሲፈጸም የአየር መንገዱ ሰራተኞች እና ኃላፊዎች የት እንደነበሩ በግልጽ ይፋ አላደረገም፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 13:46


በጋምቤላ ድልድይ ጥሶ ወንዝ የገባው አንቡላንስ ከወራት በኋላ አምስት አስከሬኖችን እንደያዘ መገኘቱ ተገለጸ

የካቲት 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በመስከረም 14 ቀን 2017 ዓ.ም በጋምቤላ ክልል ኑዌር ዞን የባሮ ወንዝ ጂካዎ ጊዜያዊ ድልድይን ጥሶ የገባው አምቡላንስ ተሽከርካሪ፤ ከወራት ፍለጋ በኋላ በውስጥ ያሉ 5 አስከሬኖችን እንደያዘ መገኘቱን የዞኑ መንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኮንግ ፔል ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በወቅቱ አንቡላንሱ አሽከርካሪውን ጨምሮ ሰባት ሰዎችን በመያዝ ከጋምቤላ ከተማ ተነስቶ ወደ ኑዌር ዞን ሲጓዝ ጅካዎ ድልድይ ጥሶ ወንዝ ውስጥ መግባቱን ይታወሳል።

በዚህም የ7 ሰዎች ሕይወት አልፎ የነበረ መሆኑን ለአሐዱ የተናገሩት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አምስት ወራት ገደማ ከተቆጠሩ በኋላ አንቡላንሱ በውስጡ አምስት አስከሬኖችን እንደያዘ መገኘቱን ተናግረዋል።

በወቅቱ በደረሰው የመኪና አደጋ የሟቾችን አስከሬን ከወንዝ ውስጥ ለማውጣት ጥረት ሲደረግ ቢቆይም፤ የባሮ ወንዝ ከመጠን በላይ በመሙላቱ ምክንያት በተለያየ ጊዜ የሁለት ሰዎች አስክሬን ብቻ መገኘቱን አስታውሰዋል።

አሁን ላይ የባሮ ወንዝ የውሀ መጠን መጉደሉን /መቀነሱን/ ተከትሎ፤ አምስት ወራት ገደማ ከተቆጠሩ በኋላ ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም አምቡላንሱ በውስጡ አምስት አስክሬኖችን እንደያዘ መገኘቱን ኃላፊው ለአሐዱ ተናግረዋል።

በአበረ ስሜነህ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 13:35


'በፖሊስ አሳስረህኛል' በሚል ቂም በመነሳት የግድያ ወንጀል የፈፅሙ እና አስክሬን የደበቁ ስድስት የአንድ ቤተሰብ አባላት በእስራት መቀጣታቸውን ተገለጸ

የካቲት 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በካፋ ዞን ዴቻ ወረዳ ቀሺ ገጠር ቀበሌ ልዩ ስፍራው የምታ ተብሎ በሚጠራበት መንደር 'በፖሊስ አሳስረህኛል' በሚል ቂም በመነሳት ግለሰብ ላይ የግድያ ወንጀል የፈፅሙ እና አስክሬን የደበቁ ስድስት የአንድ ቤተሰብ አባላት በእስራት መቀጣታቸውን የዞኑ ፍትሕ መምሪያ አስታውቋል፡፡

ሚያዝያ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ላይ ስድስት የአንድ ቤተሰብ አባላት የግል ተበዳይን መንገድ በመጠበቅ ድምፅ በሌለው ጦርና ገጀራ የግድያ ወንጀል መፈማቸውን በመምሪያው የልዩ ልዩ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ወ/ሪት ምኞት አበበ ተናግረዋል፡፡

የወንጀል ደርጊቱን የፈፀሙት በቁጥር ስድስት ሲሆኑ፤ አንደኛ ተከሳሽ ወሰኔ ቡሾ ሁለተኛ ተከሳሽ ቡሾ ኃይሌ ሦስተኛ ተከሳሽ ታመኔ ቡሾ አራተኛ ተከሳሽ ወዳጆ ቡሾ አምስተኛ ተከሳሽ ቡዛየሁ ቡሾ እና ስድስተኛ ተከሳሳሽ ማሙሽ ቡሾ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

የዴቻ ወረዳ ፖሊስ ስድስቱን ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር አድርጎ ያጣራውን የምርመራ መዝገብ መነሻ በማድረግ የዞኑ ዐቃቤ ሕግ በክስ አንድ ላይ እንዳመላከተው፤ አንደኛ ተከሳሽ ወሰኔ ቡሾ የግል ተበዳይን መንገድ በመጠበቅ " 'ስልኬን እና ገጀራ ሰርቀሀል' ብለህ በፖሊስ አሳስረህኛል" በሚል ቂም በያዘው ጦር የግራ እጁ ላይ እና በቀኝ በኩል ጎኑ ላይ አንድ ጊዜ ሲወጋው በወደቀበት በገጀራ የግራ አይኑ ቅንድብ ላይ እና መንጋጋዉ ላይ በመቁረጥ ሕይወቱ እንዲያልፍ ማድረጉ በክሱ ተጠቅሷ።

እንዲሁም ሁለተኛ ተከሳሽ ቡሾ ኃይሌ በበኩሉ ይዞት በነበረው ገመድ የሟቹን አንገቱን እና መንጋጋዉን በማሰር አስክሬኑን 400 ሜትር መሬት ለመሬት በመጎተት ጫካ ውስጥ መደበቁንና ዐቃቤ ሕግ አንደኛ እና ሁለተኛ ተከሳሾችን ሰው በመግደል ወንጀል ክስ መስርቶባቸዋል፡፡

ዐቃቤ ሕግ በ3ኛ እስከ 6ኛ ባሉ ተከሳሾችን የግል ተበዳይ ላይ ሁለቱ ግለሰቦች የግድያ ወንጀል ሲፈፅሙ እና በአስክሬኑን አንገት ገመድ አድርገው አስክሬኑን ለመሰወር ተባብረዋል እንዲሁም፤ ጎትተው ወስዶ ጫካ ውስጥ ጥለዋል በሚል አራቱን ግለሰቦች በፈፀሙት መሸሸግና አለመርዳት ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡

የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዞኑ ዓቃቤ ሕግ በሁለት ክሶች ክስ መስርቶ ያቀረበውን መዝገብ አስቀርቦ ግራ ቀኙን አስቀርቦ በማከራከር 6ቱንም ተከሳሾች በፈፀሙት የግድያ ወንጀል ክስ በማስረጃ በማረጋገጡ በሁሉም ላይ የጥፋተኝነት ብይን ሰጥቷል።

በዚሁ መሰረት የካፋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ባስቻለዉ የወንጀል ችሎት፤ አንደኛ ተከሳሽ ወሰኔ ቡሾ በ12 ዓመት ፅኑ እስራት ሁለተኛ ተከሳሽ ቡሾ ኃይሌ በ7 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ሲል ወስኗል።

ከሦስተኛ እስከ ስድስተኛ ያሉ ተከሳሾች ደግሞ እያንዳንዳቸው በ6 ወር ቀላል እስራት እዲቀጡ ዉሳኔ እንደተላለፈባቸው ዐቃቤ ህግ ምኞት አበበ ተናግረዋል ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዘግቧል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 13:16


የፍልውሃ አገልግሎት ድርጅት የቆሸሸ ውሃ አዲስ ወደ ተሠራ አስፓልት በመልቀቁ ምክንያት 300 ሺሕ ብር ተቀጣ

የካቲት 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ምሽትን ተገን በማድረግ የቆሸሸ ውሃ አዲስ ወደ ተሠራው አስፓልት የለቀቀው የፍልውሃ አገልግሎት ድርጅት 300 ሺሕ ብር መቅጣቱን አስታውቋል።

ከገንዘብ ቅጣቱ በተጨማሪም ያቆሸሸውን አካባቢ እንዲያጸዳ መደረጉን ባለስልጣኑ ገልጿል፡፡

ባለስልጣኑ የህብረተሰቡ የጋራ ሀብት የሆኑ የኮርደር ልማትና በሌሎች አካባቢ የሚገኙ መሠረተ ልማቶችን፣ ለሕዝብ የተሰሩ አረንጓዴ ስፍራዎች እና የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክቶችን ደህንነት በመጠበቅ እንዲገለገል መልዕክቱን አስተላልፏል ፡፡

አክሎም በከተማዋ ደንብ የሚተላለፉ የግልና የመንግሥት ድርጅቶች እና ግለሰቦች ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ባለስልጣኑ ህብረተሰቡ ለማንኛውም የደንብ መተላለፎች መረጃ በ9995 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪውን ማቅረቡን የባለሥልጣኑ ኮሙዩኒኬሽን መረጃ አመላክቷል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

10 Feb, 13:01


በኦሮሚያ ክልል ከነዳጅ እስከ ሸቀጥ በሕገ- ወጥ መንገድ ሲነግዱ በነበሩ ከ468 ሺሕ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

የካቲት 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኦሮሚያ ክልል በተያዘው ግማሽ ዓመት ብቻ በሕገ-ወጥ ንግድ ተሰማርተው በነበሩ ከ468 ሺሕ በላይ የሚሆኑ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን የክልሉ ንግድ ቢሮ ለአሐዱ አስታውቋል፡፡

የቢሮዉ የኢንስፔክሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ቆጲሳ፤ "በክልሉ በሕገ-ወጥ ንግድ ተስማርተው በሚሰሩ ነጋዴዎች ላይ የተወሰዱ እርምጃዎችን በተመለከተ በመሰረታዊ ሸቀጦች ከ92 ሺሕ በላይ ነጋዴዎች መመሪያውን ተላልፈው የተገኙ ናቸው" ብለዋል፡፡

በተያዘው ግማሽ ዓመት ከ11 ሺሕ 700 በላይ የንግድ ድርጊቶችን ቁጥጥር ለማድረግ ታቅዶ ከ92 ሺሕ በላይ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቀዋል፡፡

በተለይ ያለ ንግድ ፈቃድ መስራት፣ ንግድ ፈቃድ ሳያድሱ መነገድ፣ ዋጋ ሳይለጥፉ መሸጥ፣ ጊዜ ያለፈባቸውን ምርቶች በገበያ በማቅረብ እንዲሁም ዋጋ ጨምሮ በመሸጥ ሲሰሩ የተገኙ ነጋዴዎች ላይ እርምጃው መወሰዱን አስረድተዋል፡፡

የእርምጃ አወሳሰዱን በተመለከተም አስተዳደራዊ እና ሕጋዊ እርምጃ የተወሰደባቸው መሆኑን አንስተው፤ ከጹሁፍ ማስጠንቀቂያ ጀምሮ በሕግ እስከ መጠየቅ የሚደርሱ እርምጃዎች የተወሰዱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

አክለውም ክትትል በማድረግ ሕገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለማስቀረት በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኝ አንስተው፤ በዚህም ከ376 ሺሕ ሊትር በላይ የሚሆን ነዳጅ በቁጥጥር ሥር እንዲውል ማድረጉን ተናግረዋል፡፡ "ሕገ-ወጥ የነዳጅ ግብይቱን ባከናወኑ አካላት ላይም ተገቢው እርምጃም ተወስዷል"ም ብለዋል፡፡

በኦሮሚያ ክልል ሕገ-ወጥ ንግድን ለመከላከል ከሚመለከተው አካል በጋራ በመሆን እየሰሩ እንደሚገኝ እና ለማህበረሰቡ በተመጣጣን ዋጋ ተደራሽ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራሮችን በመዘርጋት እየሰሩ እንደሚገኝም ዋና ዳይሬክተሩ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Feb, 11:10


ከደረጃ በታች የሆኑ ስስ የፌስታል ምርቶች እንዳይመረቱ መከልከሉን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ

የካቲት 1/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ ውስጥ የፕላስቲክ ከረጢት ወይም "ፌስታል" በሚል የሚታወቁ የፋብሪካ ምርቶችን መጠቀም፣ ማምረት ብሎም ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባትን የሚከለክል ረቂቅ ሕግ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቅረቡ ይታወቃል።

ረቂቅ ሕጉ የፕላስቲክ ምርቶች የሚያደርሱትን ዘርፈ ብዙ የጤና፣ የአካባቢ ብክለት፣ የንጽሕናና መሠል ተያያዥ ችግሮች ለማስቀረት ያለመ ነው ተብሏል፡፡

የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን የፕላስቲክ ምርቶች በአካባቢ ላይ ብሎም በማህበረሰቡ ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ብዙ በመሆኑ ስስ የፌስታል ምርቶች እንዳይመረቱ መከልከሉን ገልጿል።

በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የአካባቢ ብክለት ቁጥጥር ቡድን መሪ ሰናይት ተስፋዬ፤ የፕላስቲክ ምርቶች በአፈር ውስጥ ተቅበረው በመቶ ዓመታት የማይበሰብሱ ከመሆናቸው ባሻገር በአፈር ውስጥ በቂ አየር እንዳይዘዋወር እና ምርት እንዳይኖር የሚያድጉ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ 

እንዲሁም በፕላስቲክ ምርቶች ውስጥ የሚገኘው 'ፒቢሲ' የተሰኘው ንጥረ ነገር በጥናት ባይረጋገጥም ሙቀት ሲነካው በመትነን ዜጎችን ለካንሰር በሽታ የማጋለጥ እድሉ ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ 

የፕላስቲክ ምርቶች የሚያደርሱት ጉዳት በተመለከተ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ  በሰፊ ንቅናቄ እየሰራበት መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ "የውፍረት መጠናቸው ከፍ ያለ ረዘም ላለ ጊዜ ማገልገል የሚችሉ የፕላስቲክ ምርቶች እንዲመረቱ እየተደረገ ነው" ብለዋል፡፡

በዚህ መስፈርት ለመስራት በርካታ ፈቃድ የጠየቁ አምራቾች መኖራቸውን አንስተው፤ ከተቀመጠው የፕላስቲክ ደረጃ በታች ያመረቱ በርካታ ፋብሪካዎች መዘጋታቸውን እና ደረጃውን ጠብቀው እንዲያመርቱ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ ምክክር የተደረገበትና ለዝርዝር ዕይታ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ የተመራው ረቂቅ ሕግ፤ "ለአንድ ጊዜ አገልግሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ" የሚከለክል ነው።

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Feb, 10:02


#አሐዱ_መድረክ

"ፖለቲካ ደም የሚያፋስስ አጥንት የሚከሰክስ አይደለም!"

ረዳት ፕሮፌሰር ጌትነት አልማው ከአሐዱ መድረክ ጋር ያደረጉት ቆይታ (ክፍል አንድ)

ውይይቱን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
https://youtu.be/VEzUDFBiakU?si=tAtTFN_PGbWEHCp-

AHADU RADIO FM 94.3

08 Feb, 08:17


የአይ ኤም ኤፍ ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ አዲስ አበባ ገቡ

የካቲት 1/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በኢትዮጵያ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ፣ የብሄራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እና የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጽም አሰፋ (ዶ/ር) አቀባበል አድርገውላቸዋል፡፡

ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ ቅድሚያ በሚሳጣቸው ፖሊሲዎች እና በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

በተጨማሪም ከግሉ ዘርፍ ተወካዮች ጋር በኢትዮጵያ ስላለው የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እና የገበያ እድሎች እንደሚወያዩ ተመላክቷል፡፡

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር እ.ኤ.አ በ2019 የተቋሙ ኃላፊ ከሆኑ በኋላ በኢትዮጵያ የሥራ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ የመጀመሪያቸው ነው፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Feb, 06:51


በተቋሙ የምርመራ መሳሪያ እጥረት በመኖሩ ታካሚዎች በቂ አገልግሎት እንደማያገኙ ተገለጸ

የካቲት 1/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በየካቲት 12 ሆስፒታል ድንገተኛ ሕክምና የሚፈልጉ ታካሚዎች ባለው የምርመራ መሳሪያ እጥረት ምክንያት በበቂ ሁኔታ አገልግሎቱን እያገኙ እንዳልሆነ ተገልጿል፡፡

በቀን ከ50 እስከ 70 የሚደርሱ ዜጎች ድንገተኛ የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል እንደሚያመሩ፤ በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ድንገተኛ እና ጽኑ ህሙሟን ህክምና ትምህርት ክፍል ኃላፊ ዶክተር ሞላልኝ ውባንተ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በድንገተኛ የትራፊክ አደጋ እና ሰው ሰራሽ አደጋዎች እንዲሁም ተላላፊ ባልሆኑ ሕመመሞች ምክንያት ታካሚዎች ለድንገተኛ ሕክምና አገልግሎት ወደ ሆስፒታሉ እንደሚመጡ ጠቁመዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም ከፍተኛ ቁጥር ባይኖራቸወም በመመረዝ ምክንያት የሚመጡ ታካሚዎች ስለመኖራቸው የገለጹ ሲሆን፤ "በምርመራ መሳሪያ እጥረት ምክንያት ታካሚዎች የምርመራ አገልግሎቱን ሌላ ቦታ እንዲፈልጉ እየተደረገ ነው" ብለዋል፡፡

አያይዘውም በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በስድስት ወራት ውስጥ ከ8 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ድንገተኛ የሕክምና አገልግሎት እንደሚሰጥ ተናግረዋል፡፡

ለምርመራ በሚያስልጉ መሳሪያዎች እጥረት ምክንያት የሕክምና አገልግሎትን ለመስጠት አስቻይ ሁኔታ አለመፈጠሩን የገለጹም ሲሆን፤ በሆስፒታሉ ያሉ የምርመራ መሳሪያዎችና ወደ ሆስፒታሉ የሚመጡ ታካሚዎች ቁጥር የተመጣጠነ አለመሆኑን ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም አደጋዎች በሚኖሩበት ጊዜ ከተጠቀሰው አሃዛዊ ቁጥር ሊጨምር የሚችልበት ሁኔታ እንዳለ ኃላፊው ጨምረው ተናግረዋል፡፡

በእሌኒ ግዛቸው
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Feb, 06:50


#ማስታወቂያ
#ADVERTISMENT

AHADU RADIO FM 94.3

08 Feb, 06:46


መልካም ቀን!
አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

AHADU RADIO FM 94.3

07 Feb, 17:20


#አሐዱ_ትንታኔ

"የአፍጋኒስታን ዜጎች ከሀገሬ ይውጡልኝ" ፓኪስታን

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/QlKUXxuZyro?si=a1qmrTuS21O32SE6

AHADU RADIO FM 94.3

07 Feb, 15:44


የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል ተገለጸ

ጥር 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በዚሁ መሰረት ፦
👉 አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር፣

👉 አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር፣

👉 አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር፣

👉 የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር፣

👉አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

👉 አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር ሆኖ በጥር ወር ሲሸጥበት በነበረው እንዲቀጥል ተወስኗል።

የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች ያልተገባ የነዳጅ ክምችት ከመያዝ እና የዋጋ ጭማሪ ከማድረግ ተቆጥበው ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ ሚኒስቴሩ አሳስበዋል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Feb, 15:25


መገናኛ ብዙኃን የቱሪዝም ኢንዱስትሪውን ለማጠናከር መወጣት የሚገባቸውን ሚና እንዳልተወጡ ተገለጸ

ጥር 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ሐብቶቿ የሚገባትን ጥቅም እንዳታገኝ መገናኛ ብዙኃን መወጣት የሚገባቸውን ሚና አልተወጡም ሲሉ የኦሮሚያ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ኮሚሽኖች ገልጸዋል፡፡

ክልሉ እምቅ የቱሪዝም አቅም እንዳለው ያስታወሱት የኦሮሚያ ክልል ቱሪዝም ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ነጋ ወዳጆ፤ "መገናኛ ብዙኃን ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጪ ጎብኚዎች ታሪክን፣ ባህልን፣ የተፈጥሮ ሃብትን ያገናዘበ የማስተዋወቅ ሥራ በበቂ ሁኔታ አልሰሩም" ብለዋል፡፡

አክለውም ለዘርፉ መነቃቃት የመገናኛ ብዙኃን ሚና ከፍተኛ በመሆኑ መገናኛ ብዙኃኑ የማስተዋወቅ እና በተለያ የውጭ ሀገር ጎብኚዎችን ለዕይታ የመጋበዝ ሚናቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ወይንቱ መልኩ በበኩላቸው፤ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በርካታ የቱሪዝም መስህቦች ቢኖሩትም በበቂ መጠን ስላልተዋወቀ የሚገባውን ያህል ጎብኚዎችን እያገኘ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡

ጎብኝዎች ኢትዮጵያን ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻ እንዲያደርጉ ለተጀመሩ ጥረቶች ሚዲያዎች የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

"ክልሉ ከፍተኛ የቱሪዝም ዓቅም ያለው ነው" ያሉት ኃላፊዋ፤ ይህንን ለመጠቀም የባለ ድርሻ አካላት ትስስር ዘላቂ አለመሆኑ እና የቁርጠኝነት ማነስም ሌላው ችግር እንደሆነ አመላክተዋል።

አክለውም "የክልሎች መንግሥታት ያላቸው ዓቅም ውስን ነው" ያሉ ሲሆን፤ ከግሉ ዘርፍ፣ ለጋሽ ድርጅቶች እና የሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ተጨማሪ ጥናት በማድረግ፣ ሥልጠና የመስጠት፣ የማስተዋወቅ ሥራ የቀጣይ ትኩረቶች መሆናቸውን ለአሐዱ ገልጸዋል።

በወልደሐዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Feb, 15:10


ሳዑዲ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ14 ሀገራት የአንድ ዓመት ቪዛን አገደች

ጥር 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሳውዲ አረቢያ ያልተፈቀደ የሃጅ ጉዞን ለመግታት ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ14 ሀገራት አዲስ የቪዛ ፖሊሲ ተግባራዊ አድርጋለች፡፡

ሳዑዲ አረቢያ ከፈረንጆቹ የካቲት 1 ጀምሮ ከ14 ሀገራት ለሚመጡ ተጓዦች ቢበዛ ለ30 ቀን ብቻ የሚቆይ ቪዛ መስጠት መጀመሯን ነው የገለጸችው።

ይህ እርምጃ በረጅም ጊዜ የጉብኝት ቪዛ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ያልተፈቀላቸው የሃጅ ተጓዦች ስጋትን ለመፍታት ታስቦ የተወሰደ መሆኑ ተነግሯል።

አዲሱ ደንብ ከአልጄሪያ፣ ባንግላዲሽ፣ ግብፅ፣ ኢትዮጵያ፣ ህንድ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ፣ ፓኪስታን፣ ሱዳን፣ ቱኒዚያ እና የመን ተጓዦችን ይመለከታል ተብሏል፡፡

በዚህም መሰረት ከእነዚህ ሀገራት ለቱሪዝም፣ ለንግድ እና ለቤተሰብ ጉብኝት የሚደረገውን የአንድ ዓመት የመግቢያ ቪዛ ላልተወሰነ ጊዜ መታገዱን ሀገሪቱ አስታውቃለች።

በተሻሻለው ሕግ መሰረት፣ ከሀገራቱ የመጡ ጎብኚዎች ለአንድ መግቢያ ቪዛ ብቻ ማመልከት የሚችሉት ለ30 ቀናት ብቻ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ነገር ግን እግዱ የሀጂ፣ ኡምራ፣ የዲፕሎማት እና የመኖሪያ ቪዛን እንደማያካትት ተገልጿል።

የሳዑዲ አረቢያ መንግሥት በሐጅ ጉዞ ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ ሲሆን፤ ለእያንዳንዱ ሀገር የተወሰነ የሐጅ ኮታን ይመድባል።

ከቅርብ ዓመታት ወዲህ፣ ቱሪስቶች እነዚህን ገደቦች በረጅም ጊዜ ቪዛ በማለፍ፤ በሀገሪቱ መጨናነቅ መፍጠራቸው አሳሳቢ ጉዳይ እየሆነ መምጣቱም ተነግሯል።

በፈረንጆቹ 2024 ከ 1 ሺሕ 200 በላይ ምዕመናን በከፍተኛ ሙቀት እና መጨናነቅ ሳቢያ ሲሞቱ፣ ባለሥልጣናቱ ያልተመዘገቡ ምዕመናን ለችግሩ መባባስ ምክንያት መሆናቸውን ተናግረዋል።

በእዮብ ውብነህ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Feb, 14:06


ከብሔራዊ ባንክ ብድር ወስደው በትግራይ ክልል እየተንቀሳቀሱ ለሚገኙ ተቋማት ተጨማሪ የብድር መክፈያ ጊዜ እንደሚያስፈልጋቸው ተገለጸ

ጥር 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ብድር ወስደው በትግራይ ክልል የተሰማሩ የንግድ እና አምራች ድርጅቶች ከዚህ በፊት ከ2 ዓመት በላይ ተራዝሞ የነበረው የብድር መክፈያ ጊዜ፤ በድጋሚ እንዲራዘም የትግራይ ክልል ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ጠይቋል፡፡

ከሰሜኑ ጦርነት በኋላ በክልሉ ለሚንቀሳቀሱ ለሁሉም ተበዳሪ ተቋማት የ18 ወራት የእፎይታ ጊዜ እንደተሰጠ የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት በሪሁን ሃፍቱ አስታውሰዋል፡፡

አቶ በሪሁን "የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከመጀመሪያው የ18 ወራት የእፎይታ ጊዜ በኋላ የአንድ ዓመት ተጨማሪ ጊዜ ቢሰጥም፤ በርካታ የንግድ ድርጅቶች የገንዘብ ግዴታቸውን መወጣት አልቻሉም" ብለዋል፡፡

" 'ይፈታል' ተብሎ የተጠበቀው ግጭትና አለመረጋጋት የንግድ እንቅስቃሴዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ በማሳደሩ ኢኮኖሚውን ጎድቶታል፣ በርካታ የንግድ ድርጅቶችም ሥራቸውን በበቂ መጠን አልጀመሩም፣ በዚህም ምክንያት ብድራቸውን መመለስ ስለማይችሉ የመክፈያ ጊዜ ማራዘምን ጨምሮ ሌሎች ድጋፎች ያስፈልጓቸዋል" ሲሉም ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

የክልሉን እና በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የንግዱ ማኅበረሰብ አባላትን ችግር ያስተዋለው የክልሉ ንግድ ምክር ቤት፤ ችግሩን ለማቃለል ከብሄራዊ ባንክ እና ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጋር እየተነጋገረ እንደሚገኝም አንስተዋል፡፡

በክልሉ ያለው የንግድ እንቅስቃሴ እና ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ እንዲያድግ የብድር መክፈያ ጊዜን ማራዘም ብቻ ሳይሆን የንግድ ተቋማቱ ተጨማሪ ብድርን ጨምሮ ሌሎች ማበረታቻዎች ሊደርግላቸው እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተውበታል፡፡

በሚካኤል ተስፋጽዮን
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Feb, 13:21


ከአንዲት እናት 20 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን ዕጢ ተወገደ

ጥር 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በማይጨው ለምለም ካርል ሆስፒታል ከአንዲት እናት 20 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም የሚመዝን አላስፈላጊ ዕጢ መወገዱን ሆስፒታሉ ገለፀ።

ታካሚዋ የቦራ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት የ63 ዓመት የዕድሜ ባለ ፀጋዋ ወይዘሮ ካሱ ረዳኢ ናቸው።

በማህጸናቸው የእንቁላል ማምረቻ አካል ውስጥ በተፈጠረ አላስፈላጊ ዕጢ ምክንያት ወደ ሆስፒታሉ ያመሩ ሲሆን፤ አንድ ሰዓት ተኩል በወሰደ የተሳካ ከባድ ቀዶ ጥገና ላለፉት 5 ዓመታት አብሯቸው የቆየው ዕጢ እንደተወገደላቸው ኢብኮ ዘግቧል።

የቀዶ ጥገና ቡድኑ በማህፀንና የወሊድ ስፔሻሊስት ዶ/ር አክሊል አለማየሁ መመራቱ ተገልጿል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Feb, 12:45


ምክር ቤቱ የአሜሪካ የእርዳታ ድርጅቶች ሥራ ማቆም አብዛኛውን ህብረተሰብ የሚጎዳ በመሆኑ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ሲል አሳሰበ

ጥር 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት በቅርቡ በዓለም አቀፍ ደረጃ የዩ ኤስ ኤ አይ ዲ ፕሮጀክቶች መቋረጡ በኢትዮጵያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማህበራት ሥራ ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽእኖ እያሳደረ መሆኑን ተናግሯል፡፡

የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አህመድ ሁሴን፤ "ለዓመታት የአሜሪካ መንግሥት ዓለም አቀፍ የልማት ተራድ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) በኢትዮጵያ ከበርካታ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ወሳኝ የልማት እና የሰብአዊ ጥረት ደጋፊ እንደነበር ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤቱ ይገነዘባል" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"ነገር ግን የድንገተኛ እገዳው ውጤት ለእነዚህ ድርጅቶች እና ለሚያገለግሉት ማህበረሰብ ክፉ እጣ ይኖረዋል" ያሉ ሲሆን፤ "ለዚህም ከፍተኛ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል" ብለዋል።

ፕሬዝዳንቱ አክለውም፤ "ምክር ቤቱ በኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ተወካይ እንደመሆኑ መጠን አሉታዊ ተጽዕኖዎችን ለመከላከል አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን እና የመቋቋሚያ መንገዶችን ከወዲሁ ማሰብ እንዲሁም ከእርዳታ መላቀቅያ መንገዶችን ማሰብ ይኖርብናል" ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ከሁለት ሳምንት በፊት በአሜሪካው ፕሬዝዳንት የተላለፈው ልዩ ትዕዛዝ በሰብዓዊ መብት፣ በዲሞክራሲ፣ በልማት፣ በትምህርት እና በጤና ዙሪያ የሚሰሩ የሲቪል ማህበራትን ተፅእኖ እያሳደረ ቢሆንም፤ ድርጅቶቹ በተለይም የሕይወት አድን ሥራዎቻቸውን እንዲተገብሩ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አጽንዖት ሰጥተዋል።

አዲሱ የትራምፕ አስተዳደር የውጭ እርዳታን ለ90 ቀናት እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ያስተላለፉ ሲሆን፤ በመላው ዓለም የሰብአዊ ድጋፍ የሚያቀርበው የአሜሪካ አለማቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት (ዩኤስኤአይዲ) በአሜሪካ መንግሥት ሥር እንደገና እንዲደራጅ ውሳኔ አሳልፈዋል።

በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሥር ዳግም ተዋቅሮ ሥራ እንደሚጀምር የሚጠበቀው የተራድኦ ድርጅቱ ድረገጽ የተዘጋም ሲሆን፤ የድርጅቱ ሠራተኞች በዋሽንግተን ወደሚገኘው ዋና ቢሮ እንዳይገቡ ክልከላ ተደርጎባቸዋል።

ይህንን ተከተሎም ለሁሉም መንግሥታዊ የጤና ቢሮዎች በጻፈ ደብዳቤ፤ በጤና ሚኒስቴር ድጋፍ ከዩኤስኤአይዲ እና ሲዲሲ ጋር በተደረገው ውል በኮንትራት የተቀጠሩ ሠራተኞች ውል መቋረጡን እና ይህን ውሳኔ እንዲያስፈፅሙ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።

ሚኒስትሩ ይህን የወሰነው ከአሜሪካ መንግሥት በ"ሲዲሲ" ወይም "ዩኤስኤአይዲ" አማካይነት በተገኘ የበጀት ድጋፍ የሚከናወን ማንኛውም ሥራም ሆነ ክፍያ፤ ከየካቲት 17 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቋረጥማሳሰቢያ ስለደረሰው መሆኑንም በደብዳቤው አሳውቋል።

በዳግም ተገኝ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Feb, 17:07


#አሐዱ_አብይ_ጉዳይ

"ሰሞኑን የተሰማው የታጠቁ ጥሪ" 

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/Yy3EwC6HynY?si=n8Jks549hjxu-Lwk

AHADU RADIO FM 94.3

01 Feb, 12:33


ደረጃን በማያሟሉ የምግብ ዘይት አምራቾች ላይ እርምጃ እየተወሰደ መሆኑ ተገለጸ

ጥር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የምግብ ዘይት ምርት ደረጃውን የጠበቅ እንዲሆን እና የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን ማሟላቱን በተመለከተ፤ የቁጥጥር እና ክትትል ሥራ መጀመሩን ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የምግብ ዘይት ደረጃን ሳያሟሉ የሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎችን ላይ እስከመዘጋት የሚደርስ የቁጥጥር ሥራ መጀመሩን፤ በሚኒስቴሩ የአምራች ኢንዱስትሪ ምርምር እና ልማት ማዕከል የምግብ እና መጠጥ ምርምር ማዕከል ተመራማሪ ፍቅሩ አበበ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"በቫይታሚን እጥረት የሚከሰቱ ዘርፈ ብዙ የጤና እክሎችን ለመቅረፍ ሲባል 'አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ላይ በብዛት አገልግሎት ላይ ይውላል' ተብሎ በሚታመነው የምግብ ዘይት ላይ፤ ቫይታሚን ኤ እና ዲ3 ለሰው ልጅ ጎጂ በማይሆን ሁኔታ በጥናት ተረጋግጦና ተመጥኖ የተቀመጠውን መጠን ያክል ይጨመራል" ሲሉም ተናግረዋል።

በምርት ሂደቱ ላይ እነዚህ ቫይታሚኖች በበቂ ሁኔታ ለህብረተሰቡ ተደራሽ እንዲሆኑ ታሳቢ ተደርጎ እንደሚጨመርና፤ ኢንዱስትሪዎች የወጣውን ደረጃ የመፈፀም ግዴታ ያለባቸው መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።

የምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን፣ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴርን ጨምሮ የክልል ጤና እና ንግድ ቢሮዎች የሚመረቱ የምግብ ዘይቶች ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ እና የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ማሟላታቸውን እንደሚቆጣጠሩም አብራርተዋል።

ይህ ምርቶችን በቫይታሚንና ሚኒራል የበለፁ እንዲሆን የሚያስገድደው ደረጃ በምግብ ዘይት ላይ ብቻ ሳይሆን፤ በሌሎች ምርቶች ላይም ተግባራዊ የሚደረግ እና የቁጥጥር ሥራው የሚቀጥል መሆኑን አፅንኦት ሰጥተውበታል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Feb, 10:02


#አሐዱ_መድረክ

"የትግራይ ችግር የሆነው ህወሓት ነው" 

በትግራይ ክልል ከሚንቀሳቀሱት የባይቶና ፓርቲ ሊቀመንበር ክብሮም በርሄ እና የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፓርቲ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ሃይሉ ከበደ ጋር የተደረገ ቆይታ (ክፍል አንድ)

ውይይቱን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!👇
https://youtu.be/204ZkidVR5M?si=IVvogXhiAZmnh43m

AHADU RADIO FM 94.3

01 Feb, 09:36


ከድምጽ ብክለት ጋር በተያያዘ ከ900 በላይ አቤቱታዎች ለባለስልጣኑ መቅረባቸው ተገለጸ

ጥር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከድምጽ ብክለት ጋር በተያያዘ 923 አቤቱታዎች መቅረባቸውን የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ባለስልጣኑ በስድስት ወራት ውስጥ በ1 ሺሕ 800 ተቋማት ላይ በድምጽ ብክለት ጋር በተያያዘ እርምጃ ስለመወሰዱም ተናግሯል፡፡

በ2017 በጀት ዓመት በስድስት ወራት ጊዜ ውስጥ ለባስልጣኑ መስሪያ ቤት ከቀረቡ ከ923 አቤቱታዎች መካከል አብዛኞቹ ከጭፈራ ቤት ጋር በተያያዘ የሚቀርብ የድምጽ ብክለት ስለመሆኑ የባለስልጣኑ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

ዋና ሥራ አስኪያጁ በስድስት ወራት ውስጥ በተከናወኑ ሥራዎች ከዚህ ቀደም ከሚተስተወሉት አንጻር ለውጦች የታዩባቸው ስለመሆናቸውም አስረድተዋል፡፡

የአካባቢ ብክለት እንዳይከሰት ከ7 ሺሕ 300 በላይ አገልግሎት ሰጪና አምራች ተቋማት ላይ የቁጥጥር ሥራ ለማከናወን እቅድ ተይዞ እንደነበር የገለጹም ሲሆን፤ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በ8 ሺሕ 772 ተቋማት ላይ የክትትል ሥራ ስለመከናወኑ ገልጸዋል፡፡

በዚህም ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ ጀምሮ እስከ ማሸግ የሚደርስ እርምጃ እንደሚሰድ ገልጸው፤ በ50 የጭፈራ ቤቶች ላይ የማሸግ እርምጃ መወሰዱን ተናግረዋል፡፡

አክለውም የግንዛቤ እጥረት እንዳይፈጠር እየተሰራ እንደሚገኝ የገለጹ ሲሆን፤ በሚስተዋሉ ለውጦች ሳይገደብ የቁጥጥር ሥራ ምሽት ላይ የሚከናወን ስለመሆኑ ገልጸዋል፡፡

በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሚከናወን ድንገተኛ የድምጽ ብክለት ቀጥጥር ላይ ተደጋጋሚ የሆነ ጥፋት በሚያደርሱ ተቋማት ላይ የንግድ ፍቃድን እስከመሰረዝ የሚደርስ እርምጃ የሚወሰድበት አሰራር ስለመኖሩም ለአሐዱ አስታውቀዋል፡፡

በእሌኒ ግዛቸው
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Feb, 08:55


ዛሬ ከቀኑ 7 ሠዓት ላይ በአሐዱ የዩትዩብ ቻናል ላይ ይጠብቁን!

👉 www.youtube.com/@AHADUTVNETWORK

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Feb, 08:00


በትግራይ ክልል በሕገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ35 ሺሕ 900 ሊትር በላይ ነዳጅ መያዙ ተገለጸ

ጥር 24/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል በተያዘው የ2017 ግማሽ ዓመት በሕገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ35 ሺሕ 900 ሊትር በላይ ነዳጅ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡

በክልሉ በተያዘው ግማሽ ዓመት ሕገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለማስቀረት ሲሰራ የነበረ ሲሆን፤ በዚህም በተደረገው ክትትልና ቁጥጥር መሰረት ነዳጁ ሊያዝ መቻሉን፤ በቢሮው የፕላን ልማትና እቅድ ዳይሬክተር አቶ ሐጎስ ግርማይ ለአሐዱ ተናግረዋል።

ዳይሬክተሩ አክለውም እንደ አጠቃላይ በክልሉ እየገባ ያለው ነዳጅ አነስተኛ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ በ6 ወራት ውስጥ ከታቀደው 67 በመቶው ብቻ ወደ ክልሉ የገባ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ይህም ካለው ፍላጎት ጋር ሲነጻጸር በጣም አነስተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ቤንዚል ከጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ክልሉ እየደረሰ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡

"ይህንን ችግር መፍትሄ ለመስጠት ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን እየተሰራ ቢሆንም፤ አሁንም በቂ የሆነ አቅርቦት የለም" ብለዋል፡፡

ባለው ነዳጅ ማህበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ ሲሆን፤ ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆንም ነዳጅ በሕገ-ወጥ መንገድ እንዳይዘዋወር ወይንም እንዳይሸጥ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡

እንደ አጠቃላይ ያሉ ግብአቶችን በመጠቀም ሕገ-ወጥ ግብይትን ለመቀነስ በቀጣይ የተለያዩ ሥራዎች እንደሚሰሩም አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Feb, 07:32


መልካም ቀን!
አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 17:15


#አሐዱ_ትንታኔ

"አሜሪካ እና ኩባን ሆድ እና ጀርባ ያደርጋቸው የትራምፕ ውሳኔ"

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/oBtvaouLbY0?si=URZeketk673X7ME3

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 15:17


በ6 ወራት ውስጥ ከ64 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ታካሚዎች የተመላላሽ አገልግሎቱ መስጠቱን አማኑኤል ሆስፒታል ገለጸ

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 በጀት በመጀመሪያ 6 ወራት ላይ 64 ሺሕ 256 ለሚደርሱ ታካሚዎች በተመላላሽ አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረጉን አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ገልጿል።

ሆስፒታሉ ለአሓዱ በላከው መግለጫ በየዕለቱ ሕክምና ሳያገኙ የተመለሱ ሕሙማን በስድስት ወራት ውስጥ አለመኖራቸውን ጠቁሟል።

በ6 ወራትም 257 የሚሆኑት የሕጻናት የአእምሮ ሕክምና ያገኙ ሲሆን፤ በሱስ ሕክምና ደግሞ 410 ለሚደርሱ ታካሚዎች የሕክምና አገልግሎቱን እንዲያገኙ ተደርጓል ብሏል፡፡
በተጨማሪም 921 ታካሚዎች በተኝቶ የአእምሮ ሕክምና አገልግሎቱን መስጠት መቻሉ ተገልጿል፡፡

"የተኝቶና ድንገተኛ የሕክምና አገልግሎት ከተሰጡት ውስጥ የማህበረሰብ ጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ የሆኑት 36 ሺሕ 300 የማህበረሰብ ክፍሎች ናቸው" ሲል ገልጿል፡፡

በተመላላሽና በተኝቶ ሕክምና በመጀመሪያ 6 ወራት ውስጥ የወንጀልና የፍትሐ ብሔር ተመርማሪ ለሆኑ 413 ሰዎች አገልግሎት ማግኘታቸውም ተመላክቷል።

በዚህም በሆስፒታሉ ጤና ጣቢያ ጥምረት ለጥራት፤ በሥነ-አእምሮ ሕክምናና የጥራት ማሻሻያ ፕሮጀክት ፅንሰ ሃሳብና ትግበራ በተመለከተ፤ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ሥር ለሚገኙ 17 ጤና ጣቢያዎች ስልጠናና ተከታታይ ድጋፍ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

የአዕምሮ ጤና አገልግሎት በጤና ተቋም ደረጃ መሰጠት የጀመረው በ1928 ዓ.ም በጣሊያን ወረራ ወቅት ነው፡፡

በወቅቱም ለሀገሪቱ ዜጎች አጠቃላይ የሕክምና አገልግሎት እንዲሰጥ ታቅዶ በጊዜው ከዋናው ከተማ ወጣ ብሎ በከተማው ጫፍ ጥቅጥቅ ባለው ገጠራማ ቦታ በተሰራውና በወቅቱ መጠሪያው ተክለሀይማኖት ሀኪም ቤት፤ በአሁኑ መጠሪያው ደግሞ አማኑኤል የአዕምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሆነው ተቋም ውስጥ አገልግሎቱን መጀመሩ ይታወቃል።

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 13:21


በአማራ ክልል ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረጉን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አስታወቀ

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአማራ ክልል ሰሜንና ደቡብ ወሎ አካባቢዎች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ለተጎዱና ለተፈናቀሉ 59 ሺሕ ለሚሆኑ ዜጎች ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሰብአዊ ድጋፍ ማድረጉን የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አስታውቋል፡፡

የማህበሩ ፕሮጀክት አስተባባሪ ዘራ ታደሰ ለአሐዱ እንደገለጹት፤ ድጋፉ የተደረገው ከዓመት በፊት በኦስትሪያ ቀይ መስቀል ማህበር በተገኘ የገንዘብ ድጎማ በተሰራ ፕሮጀክት ነው፡፡

በዚህም "በሰሜን ወሎ ጃራ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ለሚገኙ 1 ሺሕ 560 ዜጎች፣ በደቡብ ወሎ ደግሞ ተንታ እና ደሴ ዙሪያ አካባቢዎች በጦርነቱ ለተጎዱ ማህበረሰቦች በአጠቃላይ 59 ሺሕ ለሚሆኑ ተጎጂዎች ደርሷል" ብለዋል፡፡

በጦርነቱ ምክንያት በእነዚህ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ በመፈጠሩ በተለይም ሴቶች፣ ሕጻናት፣ አረጋውያንና አካል ጉዳተኞች ተጋላጭ በመሆናቸው ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራበት እንደቆየ ተናግረዋል።

በመሆኑም ለአንድ አባወራ በሦስት ዙር 21 ሺሕ ብር የሚሆን በአጠቃላይም 2 ሺሕ 560 ለሚሆኑ እማወራዎችና አባወራዎች 56 ሚሊዮን ብር የሚገመት አስቸኳይ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ ወጪ መደረጉን እንዲሁም የእርባታ ሥራ ላይ እንዲሰማሩ ማስቻሉን ገልጸዋል።

"120 ለሚሆኑ ሴቶች ደግሞ ስልጠናዎችን በማዘጋጀትና ለሥራ ማስጀመሪያ የሚሆን 5 ሚሊዮን 200 ሺሕ ብር የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ራሳቸውን እንዲቀይሩ ተሰርቷል" ሲሉም ተናግረዋል።

በተጨማሪም በጦርነቱ የፈረሱ 7 የውሀ ተቋማትን ማደስና ማስረከብ መቻሉን እንዲሁም፤ 10 ሺሕ ለሚሆኑ ዜጎች አስፈላጊ ወጪዎችን በመሸፈን ነፃ የአምቡላንስ አገልግሎት ሲሰጥ እንደቆየ አክለው ገልጸዋል።

በእርዳታ አሰጣጡ ሂደት ላይ የሚገጥሙ ችግሮች እንዳሉ የገለጹት የፕሮጀክት አስተባባሪው፤ ሆኖም ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ያለው አመለካከት ጥሩ በመሆኑ ሥራውን በሚገባ ለማከናወን እንዳገዛቸው ተናግረዋል።

በቀጣይም ከኦስትሪያ ቀይ መስቀል ማህበር በተገኘ ድጋፍ ሌሎች ሦስት ወረዳዎችን ጨምሮ ለ18 ወራት የሚቆይ ተመሳሳይ አገልግሎት እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

"በዚህ ፕሮጀክት በሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በተከሰተው ረሀብና ድርቅስ ምን አይነት ሥራዎች ተከናወኑ?" ብሎ አሐዱ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን፤ ከፕሮጀክቱ አጣዳፊ ጉዳይ ሲያጋጥም አስቀድሞ በተዘጋጀው በጀት መሰረት አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ለማቅረብ ግዢው በሂደት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 12:51


የ67 ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈውን የዋሽንግተን ዲሲው የአውሮፕላን አደጋ በሠራተኞች እጥረት ምክንያት ተከስቷል በሚለው ጉዳይ ላይ ምርመራ ተከፈተ

👉 የበረራ መረጃ መቅጃ እና ኮክፒት ድምጽ መቅጃ የሆኑት ጥቁር ብላክ ሣጥኖች ተገኝተዋል
ተብሏል

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በዋሽንግተን ዲሲ የመንገደኞች አውሮፕላን ከወታደራዊ ሄሊኮፕተር ጋር ተጋጭቶ የ67 ሰዎችን ሕይወት የቀጠፈው ክስተት በሠራተኞች እጥረት ምክንያት ተከስቷል በሚለው ጉዳይ ላይ ባለስልጣናት ምርመራ መጀመራቸው ተነግሯል፡፡

አደጋ የደረሰበት የመንገደኞች አውሮፕላን ጥቁር ሣጥኖች የተገኙም ሲሆን፤ በሠራተኞች ቁጥር እና አውሮፕላን ማረፊያው አካባቢ በተወሰኑት ውሳኔዎች ዙሪያ ጥያቄዎች እየተነሱ መሆኑ ነው የተገለጸው።

በአካባቢው ለሚበሩ ሄሊኮፕተሮች እና አውሮፕላኖች በተለምዶ ሁለት ሰዎች የአየር ትራፊክ ቁጥጥሩን የሚያከናውኑ ቢሆንም፤ ግን በአደጋው ወቅት አንድ ሰው ብቻ እንደነበር ሲቢኤስ ኒውስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል።

የብሔራዊ የትራንስፖርት ደህንነት ቦርድ (ኤንቲኤስቢ) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት በ30 ቀናት ውስጥ ይፋ እንደሚሆን አስታውቋል።

የበረራ ዳታ መቅጃ እና ኮክፒት ድምጽ መቅጃ የሆኑት ጥቁር ብላክ ሣጥኖች በበረራ ላይ ምን ችግር እንዳለ ፍንጭ ለመስጠት ይረዳሉም ተብሏል።

ሣጥኖቹ ወደ ኤንቲኤስቢ ቤተሙከራ እንደተወሰዱ እና ምርመራ እንደሚከናወን ሲቢኤስን ጠቅሶ ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።

በኒውዮርክ ታይምስ ለመጀመሪያ ጊዜ የተዘገበው የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሰው ሃይል ቁጥር ጉዳይ "ያልተለመደ አይደለም" በሚል በፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍኤኤ) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ተገልጿል።

በሬጋን ዋሽንግተን ብሔራዊ አውሮፕላን ማረፊያ አንድ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ሄሊኮፕተሮችን እና አውሮፕላኖችን የሚቆጣጠርበት አሠራር የተለመደ እና መመሪያዎችን ያልጣሰ ነው ተብሏል።

ውሃ ጠላቂዎች ከፍተኛ ቅዝቃዜ ባለው በፖቶማክ ወንዝ የተጎጂዎችን አስከሬን በመፈለግ ያሳለፉ ሲሆን፤ የማፈላለግ ሥራው ሐሙስ ማምሻውን በአደገኛ ሁኔታ ምክንያት ተቋርጧል።

እስካሁን ከአውሮፕላኑ 27 እና ከሄሊኮፕተሩ ደግሞ አንድ አስከሬን ማግኘት መቻሉም ነው የተገለጸው።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 12:26


ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆነው በመሾም ከፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀበሉ

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የቀድሞው የሰላም ሚንስትር ብናልፍ አንዷለም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ልዩ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ከኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሹመት ደብዳቤና የሥራ መመሪያ ተቀብለዋል።

የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ለአምባሳደር ብናልፍ አንዷለም የሥራ መመሪያ በሰጡበት ወቅት፤ በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የረጅም ዘመን ግንኙነት የሚመጥን ትጋትና ቁርጠኝነት የተላበሰ አመራር መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል።

ፕሬዝዳንቱ "የኢትዮጵያ አምባሳደር ሆኖ መሾም የኢትዮጵያን ሕዝብና መንግሥት ሃላፊነትና አደራ መጎናጸፍ ነው" ብለዋል።

ኢትዮጵያና አሜሪካ ከ120 ዓመታት በላይ የዘለቀ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውንም ገልጸዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው የረጅም ዘመን ግንኙነትን የሚያጠናክር ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ማድረግ እንደሚገባም አስረድተዋል።

በተጨማሪም አሜሪካ በርካታ ኢትዮጵያውያን የሚገኙባት ሀገር በመሆኗ፤ በኢትዮጵያ ልማትና እድገት ላይ በንቃት እንዲሳተፉ አምባሳደሩ ጠንካራ ስራ ማከናወን እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።

በመሆኑም በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም አሜሪካ ትልቅ እሳቤን የሚጠይቅ ዲፕሎማሲ የሚከናወንባት መሆኑን ታሳቢ ያደረገ አመራር እንዲሰጡም አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነትና ዲፕሎማሲ ወዳጅን ማብዛት ላይ የተመሰረተ መሆኑንም ገልጸዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ለማስጠበቅ፣ በቀጣናው ሰላምና ትብብርን ለመፍጠር ጠንካራ ዲፕሎማሲ እና የውጭ ግንኙነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ለጀመረችው የፖለቲካና ምጣኔ ሀብት ማሻሻያ ውጤታማነት ከአሜሪካ ጋር በትብብር መስራት እንደሚገባም ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ በቀጣይ በሰላም፣ በጸጥታና በዳያስፖራ ጉዳዮች ዙሪያ ያቀደቻቸውን ግቦች ለማሳካት አምባሳደር ብናልፍ ሚናቸው የጎላ መሆኑን ማሳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

አምባሳደር ብናልፍ አንዷለም በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት አማካኝነት ቃለ መሀላ ፈጽመዋል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 06:05


በግማሽ ዓመቱ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሱት ከ33 ሺሕ በላይ ስደተኞች ውስጥ 1 ሺሕ 60 የሚሆኑት ከፍተኛ ልዩ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ተገለጸ 

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በሕገ-ወጥ መንገድ ከሀገር ወጥተው ሳውዲ አረቢያ፣ የመን፣ ቤሩት እና የመሳሰሉ ሀገራት ውስጥ ከነበሩ ኢትዮጵያውያን መካከል 33 ሺህ 9 መቶ የሚጠጉ ስደተኞች ባለፉት 6 ወራት ወደ ሀገር ቤት መመለሳቸውን የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ከስደት ተመላሾቹ ከሳውዲ አረቢያ 31 ሺሕ 358፣ ከየመን 2 ሺሕ 304፣ ከቤሩት 237 ሰዎች በድምሩ ሕጻናትን ጨምሮ 33 ሺሕ 900 ሰዎች ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

በሚኒስቴሩ የሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከል እና የተመላሽ ዜጎች ጉዳይ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ደረጄ ተግይበሉ፤ ከተመላሾቹ መካከል 1 ሺሕ 60 የሚሆኑት ከፍተኛ ልዩ ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው የገለጹ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል 2 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሀገር መመለሳቸውን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ሥራ አስፈጻሚው እንደገለጹት፤ በአጠቃላይ በአንድ ዓመት ውስጥ ከተመለሱት 152 ሺሕ 349 ከስደት ተመላሾች መካከል 47 ሰዎች ከፍተኛ የአካል የሆነ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

አክለውም ተቋማቸው፤ ለችግር የተጋለጡ እና ልዩ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ከባለድርሻ አካላት እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ካልሆኑ ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን የድጋፍ ሥራዎች እየሰራ መሆኑንም አንስተዋል።

ከስደት ተመላሾቹ የጤና አገልግሎት እንዲያገኙ እና የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው እንደ ‹ዊልቸር› ያሉ ድጋፎችን እንዲያገኙ ከማድረግ በተጨማሪ፤ "ምግብ እና መጠለያ እንዲሁም የፋይናንስ ድጋፍ እንዲያገኙና ከቤተሰባቸው እንዲቀላቀሉ እየተደረገ ይገኛል" ብለዋል፡፡

ዜጎችን ለሕገ-ወጥ ደላሎች አሳልፈው የሚሰጡ አካላት ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ለማድረግም እየተሰራ እንደሚገኝ ነግረውናል፡፡

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 06:05


#ADVERTISMENT
#Holiday_Discount
GET 50% OFF
On All Courses

https://www.etonline.edu.et/courses/

ET Online College
Learn Anytime, Anywhere!

AHADU RADIO FM 94.3

31 Jan, 06:00


መልካም ቀን!
አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

AHADU RADIO FM 94.3

30 Jan, 17:08


#አሐዱ_ትንታኔ

"በትራምፕ ወደ ነጩ ቤተ-መንግሥት የተጋበዙት ቀዳሚው መሪ ኔታንያሁ"

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/g3VEYAIFpjQ?si=5JQkO6Os91HrT89H

AHADU RADIO FM 94.3

30 Jan, 15:05


በቦሌ ቡልቡላ 93 ማዞሪያ አካባቢ ከፍተኛ የእሳት አደጋ ተከሰተ

ጥር 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በቦሌ ቡልቡላ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 በተለምዶ 93 ማዞሪያ የሚባለው አካባቢ የእሳት አደጋ መከሰቱን አሐዱ በቦታው ሆኖ መመልከት ችሏል።

በአሁኑ ሰዓት አደጋውን ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ ሲሆን፤ አራት የእሳት አደጋ ተሽከርካሪዎች እንዲሁም አንድ የውሃ ቦቴ በቦታው መድረሳቸውን አሐዱ በስፍራው በተገኘበት ሰዓት ተመልክቷል።

የእሳት አደጋው በአካባቢው በሚገኝ ጅምር ሕንጻ ላይ ነው የተነሳው።

እሳቱን ለማጥፋት የአደጋ ሠራተኞች በስፍራው ላይ ርብርብ እያደረጉ ሲሆን፤ የጸጥታ ሃይሎች በቦታው ተገኝተው ሰዎችን ከአካባቢው ዞር እንዲሉ በማድረግ ላይ ናቸው።

በአደጋው የተጎዳ ሰው ወይም ንብረት ስለመኖሩ እስካሁን የተባለ ነገር የለም። በአካባቢው የነበሩ የአይን እማኞች እንደገለጹት እሳቱ የተነሳው ወደ 11:10 አካባቢ ነው።

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Jan, 13:46


ከአሜሪካ እና ከቻይና ፖሊሶች ጋር ውድድሩን የሚያደርገው የፌደራል ፖሊስ ስዋት ቡድን በዱባይ ልምምድ ማድረግ ጀመረ

ጥር 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የተባበሩት ዐረብ ኢምሬቶች ባዘጋጀችው የዓለም አቀፍ የ2025 ፈጣን ምላሽ አሰጣጥ ውድድር (SWAT Challenge) ላይ ለመወዳደር ወደ ዱባይ ያቀናው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ስዋት ቡድን ልምምድ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

በዚህ የዓለም አቀፍ የ2025 ፈጣን ምላሽ አሰጣጥ ውድድር ላይ ለመወዳደር ወደ ዱባይ ያቀናው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ስዋት ቡድን በአልሩዋይ ከተማ በሚገኘው የስዋት ቻሌንጅ ማሰልጠኛ ማሰልጠኛ ማዕከል ልምምድ እያደረገ መሆኑ ነው የተገለጸው።

የስዋት ቡድኑ፤ በታክቲካል ኦፕሬሽን ቻሌንጅ፣ በጥቃት ቻሌንጅ፣ በVIP አመራር የማዳን ተልዕኮ፣ በከፍተኛ ታወር መውጣትና መውረድ እንዲሁም በመሰናክል ኮርስ ዘርፎች እንደሚወዳደር ተገልጿል።

ውድድሩ እ.ኤ.አ የካቲት 1-5 እንደሚካሄድም ታውቋል።

በውድድሩም አሜሪካና ቻይናን ጨምሮ ከ50 ሀገራት የተውጣጡ ከ120 በላይ የSWAT ቡድኖች እንደሚሳተፉ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መረጃ አመላክቷል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Jan, 13:27


የሶማሊያ ጦር 16 የአል-ሸባብ አሸባሪዎችን መግደሉን አስታወቀ

ጥር 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሶማሊያ ጦር ባለፈው ማክሰኞ በሂራን ክልል ምስራቃዊ ክፍል በወሰደው እርምጃ 16 የአል-ሸባብ ብድን አባላትን መግደሉን የሀገሪቱ የመንግሥት ሚዲያዎች ዘግበዋል፡፡

ጦር ኃይሉ በሀገሪቱ ከሚገኙ የሰላም አስከባሪ ሃይሎች ጋር በመቀናጀት ከአልቃይዳ ጋር ግንኙነት ያለውን የአል ሸባብ ታጣቂዎች ቡድን ለማጥፋት በሂራና ክልል የጀመረውን መጠነ ሰፊ ዘመቻ አጠናክሮ መቀጠሉ ነው የተገለጸው፡፡

በዚህም የሀገሪቱ የጸጥታ ሃይሎች ቢራ ያባል፣ ቡር አቦቶ፣ ኤጋ ጋልማአይ፣ ጂድቺላን እና ካዶው ጉሬይ ጨምሮ በርካታ ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን በተሳካ ሁኔታ መያዛቸው ተነግሯል።

በዚህ ወታደራዊ ዘመቻም 16 የሚደርሱ የሽብር ቡድኑን ታጣቂዎች መግደሉን ጦሩ አስታውቋል፡፡

ሠራዊቱ እስካሁን እያደረገ ያለው ዘመቻ ሶማሊያን ከአክራሪ ቡድኖች ሙሉ በሙሉ ነፃ ለማውጣት እና የሶማሊያ ዜጎችን ዘላቂ ሰላምና ደህንነት ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑን ተገልጿል።

ሀገሪቱ ለዓመታት ከሽብር ቡድኖች ጋር እየታገለች ብትገኝም፤ የዜጓቿን ሰላምና ደህንነት ከማስጠበቅ አኳያ እዚህ ግባ የሚባል ለውጥ ማምጣት አልቻለችም ነው የተባለው፡፡

አል-ሸባብ ከአሮፓዊያኑ 2007 ጀምሮ ከሶማሊያ መንግሥትንና በሀገሪቱ ከሰፈረውን የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪዎች ጋር እየተዋጋ ይገኛል።

በደረጄ መንግስቱ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Jan, 11:58


የጥራት ደረጃን ያላሟሉ ከ932 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ የተለያዩ ምርቶች ወደ ሀገር እንዳይገቡ መደረጉ ተገለጸ

ጥር 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 በጀት ዓመት 6 ወራት ውስጥ አስገዳጅ ደረጃ ከወጣባቸውና የጥራት ቁጥጥር ከተደረገባቸው ገቢ ምርቶች ውስጥ የኢትዮጵያን የጥራት ደረጃ ያላሟሉ ከ9 መቶ 32 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ ምርቶች ወደ ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

ማንኛውም ምርት ወደ ሀገር ውስጥ ሲገባ ሀገሪቷ ባስቀመጠችው ደረጃ መሰረት ድንበር ላይ ፍተሻ እንደሚደረግ ለአሐዱ የተናገሩት በሚኒስቴሩ የሀገር ውስጥ ንግድና የሸማች ጥበቃ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሊቁ በነበሩ ናቸው፡፡

መሪ ሥራ አስፈፃሚው በርካታ ምርቶችም የኢትዮጵያ ደረጃ ባለማሟላታቸው ሀገር ውስጥ እንዳይገቡ የማድረግ ሥራ መሰራቱንም አንስተዋል፡፡

የኢትዮጵያን የጥራት ደረጃ ሳያሟሉ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምርቶችም፤ በየፍተሻ ጣቢያው የሚገኙ ባለሙያዎች ኃላፊነታቸውን ከመወጣት አንፃር በሚፈጥሩት ክፍትት እንደሆነ ተናግረዋል።

በቅርቡ ከሁለት ሳምንት በፊትም አስገዳጅ የኢትዮጵያን ደረጃ ያላሟላ የተሸከርካሪ ባትሪ ወደ ሀገር እንዲገባ ያደረጉ ባለሙያዎች ከሥራ መሰናበታቸውንና ጉዳያቸው በሕግ እየተጣራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

መሰል ሕገ-ወጥ ሥራ ላይ የተሰማሩ አካላት ላይ ሚደረገው የቁጥጥር ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አንስተዋል፡፡

በጠቅላላው ባለፉት 6 ወራት ውስጥ ከ1 ሚሊዮን 700 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ ገቢ እቃዎች ላይ የጥራት ቁጥጥር ሥራ ስለመደረጉም ኃላፊው አመላክተዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Jan, 11:46


ምክር ቤቱ የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ

ጥር 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 17ኛ መደበኛ ስብሰባው፤ ለመምህርነት ሙያ ይበልጥ ትኩረት እንዲሰጥ የሚያደርገውን የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጅ አጽድቋል።

ምክር ቤቱ ከሰው ሀብት ልማት ስራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ረቂቅ አዋጁን አስመልክቶ የቀረበለትን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አዳምጧል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ(ዶ/ር) "ረቂቅ አዋጁ አጠቃላይ ትምህርትን በፍትሃዊነት ተደራሽ ማድረግ ያስችላል" ብለዋል።

በተጨማሪም "የመንግሥትን የትምህርት ስርዓት ታሳቢ ያደረገ የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖር ያደርጋል" ነው ያሉት።

ረቂቅ አዋጁ ለመምህርነት ሙያ ይበልጥ ትኩረት እንዲሰጥ እንደሚያደርግ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ረቂቅ አዋጁ ሴት መምህራንን ወደ አመራርነት እንዲመጡ የሚያበረታታና አካቶ ትምህርትን አስገዳጅ የሚያደርግ መሆኑንም አስታውቀዋል።

በረቂቅ አዋጁ ላይ ቋሚ ኮሚቴውና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ሰፊ ውይይት ማድረጋቸውንና በዚህም 77 አንቀፆች ላይ ማሻሻያ መደረጉን ማንሳታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የአጠቃላይ ትምህርት ረቂቅ አዋጁ ላይ የምክር ቤቱ አባላት ሰፊ ውይይት ካደረጉ በኋላ በ2 ተቃውሞ በ10 ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፅ አዋጅ ቁጥር 1368/2017 ሆኖ ጸድቋል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b

AHADU RADIO FM 94.3

30 Jan, 10:14


#አሐዱ_ትንታኔ

"ጥግ እና ጥግ ይዘው የሚካሰሱት የሩስያ እና ዩክሬን መሪዎች"

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/VGxs5YxG3DI?si=OEjB_bCeWebSE6B9

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 17:31


#አሐዱ_ከመሪዎች_ዓለም

"ቅዱስም እስረኛም የሆኑት ሰው"

ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/iFPDtbwp86g?si=kfXBrbbSC_oCzsWV

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 13:34


ብልፅግና ፓርቲ ሰላማዊ ሀገርን ለትውልድ ማሻገር ላይ ትኩረት ሰጥቶ ሊሰራ ይገባል ተባለ

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ብልፅግና ፓርቲ ከተመሰረተ ጊዜ ወዲህ 'ታሪካዊ' ሲል የጠራውን የመጀመሪያ ጠቅላላ ጉባኤውን በ2014 ዓ.ም ማከናወኑ የሚታወስ ሲሆን፤ ከቀናት በኃላ ደግሞ ከአርብ ጥር 23 እስከ ጥር 25 ቀን 2017 ድረስ ሁለተኛው ጠቅላላ ጉባኤውን እንደሚያድርግ ይጠበቃል፡፡

ፓርቲው ይህንን ጉባኤውን የሚያደርገው በተለይም በሀገር ደረጃ ያጋጠሙት የሰላም እና ጸጥታ ችግሮች እንዲሁም የኑሮ ውድነት ዜጎች እየፈተነ ባለበት ወቅት ላይ መሆኑ ይታወቃል፡፡

አሐዱም "ለመሆኑ የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ጠቅላላ ጉባኤ በተለይም በኢትዮጵያ የሰላም እና ፀጥታ ጉዳይ ላይ ምን ዓይነት ውሳኔዎች ሊተላለፉ ይገባል?" ሲል ፖለቲከኞችን ጠይቋል፡፡

"ብልፅግና ፓርቲ በሁለት ጉዳዮች ላዩ ትኩረት ሊያደርግ ይገባል" የሚሉት ፖለቲከኛ እና የእናት ፓርቲ አባሉ አቶ ጌትነት ወርቁ፤ "በተለይ የዜጎችን ደህንነት መጠበቅ እና የዜጎች የከፋ የኑሮ ውድነትን መቀነስ ላይ ማተኮር አለበት" ብለዋል፡፡

"አሁን በኢትዮጵያ ያለው ፖለቲካዊ ችግሮች አሁን ካለበት በዘለለ የከፋ ችግር ሳያመጣ መንግሥት ጠንከር ብሎ ወደ ድርድር መግባት ይገባዋል" ሲሉም ፖለቲከኛው አሳስበዋል፡፡

የመንግሥት ተቀዳሚ ሥራ የዜጎች ደህንነት ማስጠበቅ መሆኑን የገለጹት አቶ ጌትነት፤ በዚህ ጉባኤም የፓርቲው ትኩረት በዋናነት መሆን ያለበት ይሄው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

አቶ ጌትነት በተለይም በአሁን ሰዓት በሀገር አቀፍ ደረጃ ያለውን ችግር መፍታት ባለመቻሉ ዜጎች በተለይም ወጣቶች ስደትን ምርጫቸው እያደረጉ መሆኑን በመግለፅ፤ ጉባኤው ለነዚህ ችግሮች መፍትሄ የሚሰጥ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባኤ በዋናነት በሰላምና ደህንነት በተለይም ወደ ድርድር በሚያመጡ መንገደች፣ በኑሮ ውድነት እና ወቅታዊ የትግራይ ፖለቲካዊ ቀውስ ላይ አቅጣጫዎች ያስቀምጣል ብለው እንሚጠብቁ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ሌላው ከአሐዱ ጋር ቆይታ ያደረጉት የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራሲ ፓርቲ (ኢሶዴፓ) ምክትል ሊቀመንበር ዶክተር ራሄል ባፌ ሲሆኑ፤ እሳቸውም "በሀገር ደረጃ ሰላምና ፀጥታን ለማምጣት የሁሉም አካላትን ርብርብ የሚጠይቅ ጉዳይ ነው" ብለዋል፡፡

"ፓርቲው በዚህ ጉባኤው በዋናነት የሕዝቡን ደህንነትና ሰላም ማስጠበቅ ያለበት አካልን የሚመራ ፓርቲ በመሆኑ፤ በትክክለኛ እና ሀቀኝነት ሰላምን ለማምጣት መስራት አለበት" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ጉባኤው የብልፅና ፓርቲ የፓርቲውን ጉዳይ የሚመክረበት ቢሆንም ሀገርን የሚመራ መንግሥትን የሚመራ ፓርቲ እንደመሆኑ፤ በተለይም ግጭት ውስጥ ካሉ አካላት ጋር እውነተኛ ስምምነት ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

አሐዱ ያነጋገራቸው ፓርቲዎች ብልፅግና ፓርቲ በጉባኤው በተለይም ሕዝብን ሰላምና ደህንነት አንፃር አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ብለው እንደሚጠበቁ ገልጸዋል፡፡

ብልፅግና ፓርቲ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ፈተና የገጠመው ፓርቲ መሆኑ የሚገለፅ ሲሆን፤ በተለይም ግጭት፣ ጦርነት እና የኑሮ ውድነት ፈተናዎቹ እንደነበሩ ይገለጻሉ፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 11:39


የተሰጠው ትኩረት አነስተኛ በመሆኑ በኢትዮጵያ የሚጥል በሽታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተገለጸ

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሚጥል ሕመምን ለማከም የሚችሉ በቂ የጤና ባለሙያዎች አለመኖር፣ የመድኃኒት አቅርቦት ችግር እና ተያያዥ ጉዳዮች ለሕመሙ ትኩረት እንዳይሰጥ በኢትዮጵያ ኬር ኤፕለፕሲ ማሕበር ለአሐዱ አስታውቋል።

በተጨማሪም በህብረተሰቡም የሚጥል ሕመም እንደሚታከም እንዳያውቅ ማድረጉ የበሽታው መባባስ መንስኤ መሆኑን ማህበሩ ገልጿል።

ለሕመሙ የሚሰጠው የተሳሳተ ግንዛቤ በተለይ የሚጥል ሕመምን ከመንፈስ ጋር በማገናኘት እና ወደ ሕክምና ቦታ አለመውሰድ ዋነኛ ችግሮች መሆናቸውን የማሕበሩ ሥራ አስኪያጅ አብይ አስራት ተናግረዋል።

"የሚጥል በሽታ መንስኤዎች እስካሁን በግልጽ የማይታወቅ ሲሆን፤ በብዛት ግን በተፈጥሮ፣ እንቅልፍ በማጣት፣ በራስ ቅል ላይ በሚደርሱ አደጋዎች እና ኢንፌክሽኖች፣ በስትሮክ እና በሌሎች መሰል ምክንያቶች ሳቢያ ይከሰታል" ብለዋል።

ምን ያህል የሚጥል በሽታ ታማሚዎች እንዳሉ በቂ ጥናቶች አለመኖር፣ የነርቭ ሕመም ሆኖ ሳለ በአእምሮ ሕመም ሥር መደረጉ ሕክምናውን ተደራሽ እንዳይሆን ካደረጉ ምክንያቶች ውስጥ አስቀምጠዋል፡፡

ሥራ አስኪያጁ አያይዘውም የሚጥል ሕመምን ማከምና መንከባከብ የሚያስችል የጤና ባለሙያ ቁጥርን ለማብዛት እንዲሁም ሕመሙ እንዳይከሰት ለመከላከል በጤና ተቋማት ውስጥ ለሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ስልጠና እንደሚሰጥም ተናግረዋል።

በባለድርሻ አካል ትኩረት እንዲሰጥ፣ በሕብረተሰቡ ዘንድ ጎጂ ልማዳዊ አስተሳሰብ እንዲቀየር እየተሰራ ነው ብለዋል።

በኢትዮጵያ ውስጥ ከ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የዚህ በሽታ ተጠቂ እንደሆኑ የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመላከተ ሲሆን፤ ከእነዚህም ታማሚዎች ውስጥ ሕክምና የሚያገኙት 5 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸውን ጠቁመዋል።

ኬር ኢፕለፕሲ ኢትዮጵያ ከተቋቋመ 9 ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን፤ የሚጥል ሕመም ያለባቸው ታማሚዎች እንደማንኛውም ሰው መገለል ሳይደርስባቸው የሚኖሩበት መንገድ ለማመቻቸት አላማው አድርጎ በመንቀሳቀስ ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል።

በወልደሐዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 11:07


ትራምፕ መንግሥት የፆታ ለውጥ ለሚያደርጉ ወጣቶች ይሰጥ የነበረው ድጋፍ እንዲቋረጥ ልዩ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸው ተገለጸ

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ባለፈው ሳምንት ወደ ዋይት ሀውስ የገቡት የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በርካታ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ተፅዕኖ ያላቸው ውሳኔዎችን ያስተላለፉ ሲሆን፤ ትላንት ደግሞ መንግሥት የሥርዓተ-ፆታ ለውጥ ለሚያደርጉ ከ19 ዓመት በታች ለሆኑት ወጣቶች ይሰጥ የነበረውን ድጋፍ እንዲያቋርጥ ወስነዋል፡፡

ትራምፕ ከዚህ በኋላ "የአሜሪካ መንግሥት የፆታ ለውጥን በገንዘብ አያስተዋውቅም፣ አያበረታታም፣ አይደግፍምም" ሲሉም ገልጸዋል፡፡

ፕሬዝደንቱ ይህን ያስተላለፉትን ውሳኔ የአሜሪካ የጤናና የሰብዓዊ አገልግሎት ዲፓርትመንት ተፈፃሚ  እንዲያደርገው አቅጣጫ መስጠታቸውን አልጄዚራ ዘግቧል፡፡

ይህን ተከትሎም የትራንስጀንደር የመብት ተሟጋች ቡድን፤ "የትራምፕ ንግግር ‘በጣም አስፈሪ ትክክል ያልሆነ፣ ወጥነት የሌለው እና ጽንፍ የያዘ ነው" ሲል ገልጿል።

ይህ የትራምፕ ትዕዛዝ በስርዓተ-ፆታ ለሚሰቃዩ ወጣቶች የተለያዩ ሕክምናዎችን እና ሂደቶችን ይሸፍናል የተባለ ሲሆን፤ ይህም ባዮሎጂካዊ ጾታቸው ከቀየሩት የጾታ ማንነታቸው ጋር የማይዛመድ ሰዎች የሚሰማቸውን ጭንቀት ለማስውገድ እንደሚያግዝ ተመላክቷል።

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ‘’ወንድና ሴት የሚባሉ ሁለት ፆታዎች አሉ፤ እነርሱም ሊቀየሩ አይችሉም” ሲሉ በበዓለ ሲመታቸው ቀን መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በዩናይትድ ስቴትስ በሥርዓተ-ፆታ መዛባት ምክንያት ለተለያዩ ጭንቀቶች የተዳረጉ ወጣቶች ቁጥር ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በብዙ እጥፍ መጨመሩ ተገልጿል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 10:10


#አሐዱ_ትንታኔ

"ስልጣን በያዙ በጥቂት ቀናት ውስጥ ከመቶ በላይ ትዕዛዞችን ያስተላለፉት ትራምፕ"

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/fac9GUxVxc8?si=EKK_MKpq63c8P74R

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 09:52


ብልጽግና ፓርቲ 15 ነጥብ 7 ሚሊየን አባላት እንዳሉት የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ተናገሩ

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ሕዳር 6 ቀን 2012 ዓ.ም. ባደረገው ስብሰባ የፓርቲዎች ውህደትን በአብላጫ ድምጽ ማድቁን ተከትሎ፤ በርካታ ፓርቲዎች ከህወሓት ውጪ ወደ ውህደቱ የተቀላቀሉ ሲሆን ብልጽግና ፓርቲ በይፋ ተመስርቷል። በዚህም በርካታ የፓርቲ አባል እንዳሉት ሲገለጽ ቆይቷል።

የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ አደም ፋራህ በሰጡት መግለጫ፤ የፓርቲው አባላት ቁጥር 15 ነጥብ 7 ሚሊየን መድረሳቸውን ገልጸዋል።

ኃላፊው ይኼን የገለጹት የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛው መደበኛ ጉባኤውን በተመለከተ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ነው።

ብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል ከአርብ ከጥር 23 - 25 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በአድዋ ድል ሙዚየም ይካሄዳል።

በጉባኤው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት፣ የኢንስፔክሽን እና ስነምግባር ኮሚሽን እንዲሁም የጉባኤ ተሳታፊዎች በአጠቃላይ 1 ሺሕ 700 የሚሆኑ ሰዎች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።

የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች እና 15 የሚሆኑ የውጭ ሀገራት እህት ፓርቲዎች እንደሚሳተፉ አንስተዋል።

ለሦስት ቀናት በሚቆየው በጉባኤ በመጀመሪያው ጉባኤ የተቀመጡ ጉዳዮች ተፈጻሚነታቸው እንዲሁም መሻሻል የሚፈልጉት ስራዎች ማሻሻል ላይ እንደሚያተኩር ተገልጿል።

እንዲሁም ፓርቲውን ብሎም የመንግሥትን አቅም የሚያጠነክሩ ውሳኔዎችን አቅጣጫዎች ይቀመጣሉ ተብሏል።

"ዘላቂ ሰላምን ብሎም የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስጠበቅ የሚችሉ ውሳኔዎችን ይሰጣሉ ሲሉ" የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገልጸዋል።

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 09:43


የስንዴ ዱቄት አምራች ኢንዱስትሪዎች የተለያዩ በቫይታሚን እና በማዕድን የበለጸጉ ግብዓቶችን በመጨመር እንዲያመርቱ የሚያስገድድ ሕግ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ ተነገረ

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ የሚገኙ የስንዴ ዱቄት አምራች ኢንዱስትሪዎች በሚያመርቱት ምርት ውስጥ የተለያዩ በቫይታሚን እና በማዕድን የበለጸጉ ግብዓቶችን በመጨመር እንዲያመርቱ የሚያስገድድ ሕግ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በሚኒስቴሩ የአምራች ኢንዱሰትሪ ምርምር እና ልማት ማዕከል የምግብ እና መጠጥ ልማት ማዕከል ተመራማሪ ፍቅሩ አበበ አምራች ኢንዱስትሪዎቹ ፎሊክ አሲድን ጨምሮ ቫይታሚን ቢ ኮምፕሌክስ፣ ቫይታሚን ዲ፤ ዚንክ እንዲሁም ሌሎች የቫይታሚን እና የማዕድን አይነቶችን የስንዴ ዱቄት ምርታቸው ላይ በመጨመር የማህበራዊ ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ እየተደረ መሆኑን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

አሐዱም "ከስንዴ ውጪ ሁሉም ማህበረሰብ የሚጠቀማቸውን የምግብ ግብዓቶች ላይ ለምን ተጨምሮ የሚሰራበት አካሂድ የለም ወይ?" ሲል አቶ ፍቅሩን ጠይቋል፡፡

በምላሻቸውም ስንዴ 37 በመቶ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብቻ እንደሚጠቀመው በማስታወስ፤ "በሌሎች ግብዓቶች ላይ መጠቀም ያልተቻለው የምርት ሂደታቸው ማዕድኖች እና ቫይታሚኖችን ለመጨመር አስቸጋሪ መሆኑን ነው" ብለዋል፡፡

እንደ ምሳሌነትም የጤፍ አመራረት እና ወደ ዱቄት የሚቀየርበት አካሄድ ለአሰራር እንደማይጋብዝ ተናግረዋል፡፡

የስንዴ ዱቄት አምራቾች ላይ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ምርቶች ላይም መሰል ተግባራት እንደሚሰሩና የተለያዩ ጥናቶች እየተካሄዱ እንደሚገኝም ጨምረው ተናግረዋል፡፡

በዳግም ተገኝ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 08:51


በኮንጎ እየተካሄደ ባለው ውጊያ አራት ተጨማሪ የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች መገደላቸው ተነገረ

👉 የተለያዩ ሀገራት ኤምባሲዎች በተቃዋሚዎች ጥቃት ተሰንዝሮባቸዋል

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኮንጎ ጦር ከኤም 23 ታጣቂ ቡድን ጋር ባደረገው ውጊያ አራት ተጨማሪ የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች መገደላቸው ተነግሯል።

ወታደሮቹ የተገደሉት በምስራቃዊ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሀገሪቱ ጦር ከኤም 23 ታጣቂ ቡድን ጋር በቀጠለው ውጊያ ነው ተብሏል።

ባለፈው ሰኞ በጎማ አውሮፕላን ማረፊያ አካባቢ በተካሄደው ጦርነት ሦስት ወታደሮች ሲገደሉ፤ አንድ ሌላ ደግሞ ቀደም ሲል በተደረገው ጦርነት ቆስሎ መሞቱን የደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ መከላከያ ሠራዊት ባወጣው በመግለጫው አስታውቋል።

መከላከያ ሠራዊቱ አርብ ዕለት ከኤም 23 ሃይሎች ጋር በተፈጠረ ግጭት ሁለት የተባበሩት መንግሥታት የሰላም አስከባሪ ሃይል አባላትን ጨምሮ ዘጠኝ የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች መገደላቸውን ማስታወቁ ይታወሳል።

በሩዋንዳ መንግሥት የሚደገፈው ኤም 23 በማዕድን የበለጸገውን ሰፊ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ክፍል እንዲሁም በሀገሪቱ ምስራቃዊ ክፍል የክቡ ክፍለ ሀገር ዋና ከተማ የሆችውን ጎማን መቆጣጡን ተከትሎ፤ በተቀሰቀሰው አመፅ የአሜሪካና የኬኒያን ጨምሮ ስድስት ሀገራት ኤምባሲዎች ላይ ከባድ ጥቃት ተፈጽሟል።

በሀገሪቱ ዋና ከተማ ኪንሻሳ የሩዋንዳን ጨምሮ የበርካታ ምዕራባውያን እና አፍሪካ ኤምባሲዎች ውጭ ላይ ተቃዋሚዎች ተሰብስበው ኤምባሲዎችን በእሳት አቃጥለዋል።

በተጨማሪም የፈረንሳይ ኤምባሲ ላይ በተቃዋሚዎች ጥቃት መድረሱን የፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለሲኤንኤን ተናግሯል፡፡ ነገር ግን ተቃዋሚዎች ወደ ኤምባሲው መግባት አልቻሉም ብሏል፡፡

በትናንትናው ዕለት በኪንሻሳ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በበኩሉ፤ የአሜሪካ ዜጎች ከተማዋን ለቀው እንዲወጡ መክሯል።

በዚህም "በኪንሻሳ ከተማ እየደረሰ ያለው ሁከት እየጨመረ በመምጣቱ በከተማዋ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጎቹ ወደ መጠለያ ቦታ እንዲገቡ" ያሳሰበ ሲሆን፤ የተለያዩ አማራጮች ሲገኙ ከአገሪቱ እንደሚወጡ ገልጿል፡፡

ኤም 23 አማጺ ቡድን ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሰዎች መኖሪያ በሆነችው ጎማ ከተማ ላይ የሚያደርገውን ግስጋሴ እንዲያቆም የዓለም ማህበረሰብ ጥሪ ቢቀርብለትም፤ አሁንም ጦርነቱ መቀጠሉ ነው የተገለጸው።

ሞስኮ በበኩሏ የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ግጭት እንዲቆምና ንግግር እንዲጀመር ጥሪ አቅርባለች።

በአበረ ስሜነህ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 07:59


በኢትዮጵያ 97 በመቶ ሕዝብ የሚሆነው በአዮዲን የበለፀገ ጨው የማግኘት እድል እንዳለው ተገለጸ

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከኢትዮጵያ ሕዝብ 97 በመቶ የሚሆነው በአዮዲን የበለፀገ ጨው የማግኘት እድል እንዳለው የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል።

ከ2015 በፊት በኢትዮጵያ ያለው የአዮዲን እጥረት ከፍተኛ የነበረ ሲሆን፤ ችግሩን ለመፍታት በተሰራ ሥራ ብዙ ለውጦች መምጣታቸውን የባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የኢንስፔክሽንና ሕግ ማስፈፀም ሥራ አስፈፃሚ ሙላት ተስፋዬ ለአሐዱ ገልጸዋል።

ከ2015 በፊት በአዮዲን የበለፀገ ጨው 5 በመቶ ብቻ የሚያገኝ የነበረ ሲሆን፤ አሁን ላይ 97 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ በአዮዲን የበለፀገ ጨው የማግኘት እድል እንዳለው የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባጠናው ጥናት መረጋገጡን ተናገረዋል።

ይህም በየሸቀጣሸቀጥ መደብሮችና ሱቆች ላይ በሚገኝ ጨው ላይ ተመርምሮ ቢያንስ አዮዲን አላቸው ወይስ የላቸውም የሚለው ብቻ የተረጋገጠ መሆኑን ሥራ አስፈፃሚው አሳውቀዋል።

ነገር ግን የትኞቹ የጨው አይነቶች በደረጃው መሰረት ወይም መጠቀም የሚጠበቅባቸውን የአዮዲን መጠን በትክክል ተጠቅመዋል ከሚል ቁጥጥር አንፃር ክፍተት መኖሩን አክለዋል።

ሆኖም ግን በተለያየ መንገድ ገበያው ላይ በተጠና ጥናት 18 በመቶ የሚሆነው ጨው ያለው የአዮዲን መጠን ከደረጃ በታች መሆኑን በማንሳት፤ እንዲህ አይነት ክፍተት በሚፈጥሩት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ አሳውቀዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

29 Jan, 06:32


"ሴቶች በፖለቲካ ዘርፍ ለመሳተፍ ፍላጎት የላቸውም ብሎ መደምደም አይቻልም" የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ጥር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ምዝገባ እና ሥነ-ምግባር አዋጅ 1162/2011 ለማሻሻል ከፓርቲዎች ጋር ውይይት እያደረገ የሚገኝ ሲሆን፤ በተለያዩ የረቂቁ አንቀፀች ላይ ሀሳቦች እየሰጡ ይገኛል፡፡

ከአሐዱ ጋር ቆይታ የነበራቸው የአገው ብሔራዊ ሸንጎ ሊቀመንበር አላማርው ይርዳው፤ "በአዋጁ ላይ የሴቶችን ተሳትፎ በሚመለከት በአመራር ላይ እስከ 30 በመቶ ሴቶች መደረግ አለባቸው የሚለው ሀሳብ ተገቢ አይደለም" ብለዋል፡፡

ሊቀመንበሩ የሴቶች ፖለቲካዊ ተሳትፎ የሚደገፍ መሆኑን ያነሱ ሲሆን፤ በቅርቡ ባደረጉት ጠቅላላ ጉባኤ ከዘጠኙ ሥራ አስፈፃሚ አምስቱ ሴቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

"ነገር ግን ባለው ተጨባጭ ነባራዊ ሁኔታ ሴቶችን 20 እና 30 በመቶ በአመራር ላይ ማድረግ ይቻላል ወይ?" ሲሉ ይጠይቃሉ፡፡

"በተለይም ሴቶች ካለባቸው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተፅዕኖ አንፃር በዚህ ደረጃ ሴቶች የፖለቲካ አመራር መደረግ አለባች ተብሎ በአወጁ ላይ መቀመጡ ነባራዊ ሁኔታውን ያላገናዘበ ነው" ሲሉ ገልጸውታል፡፡

ምርጫ ቦርድ እያሻሻለ በሚገኘው አዋጅ ላይ፤ 'በተለይም በምርጫ የሚወዳደር አንድ ፓርቲ ቢያንስ 20 በመቶ ዕጩዋቹ ሴቶች መሆን አለባቸው' ይላል፡፡

በሌላ በኩል ረቂቅ አዋጁ በፖለቲካ አመራርነትም የሴቶችን ተሳትፎ የሚያሳድግ ብሎ ያመነውን 'ሴቶች በፖለቲካ አመራርነት ቢያንስ 30 በመቶ ድርሻ እንዲኖራቸው' ሲል ያስቀምጣል፡፡

አሐዱም ለመሆኑ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች የተነሱ በተለይም ሴቶች በገዢ ፓርቲዎች ላይ ካልሆነ በተፎካካሪ ፓርቲዎች ላይ የመሳተፍ ፍላጎት የላቸውም የሚለውን ሀሳብ በሚመለከት ቦርዱን ጠይቋል፡፡

የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ 'ሴቶች በፖለቲካ ፓርቲ ላይ ሊሳተፉ አይችሉም' የሚል ጥናት ላይ ያልተመሰረተ ሀሳብ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ከሴት ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጋር በተያያዘ ይህ አስተሳሰብ መታረም ያለበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተለይም ረቂቁ ገና ውይይት ላይ ባለበት ሁኔታ 'መሳተፍ አይፈልጉም' የሚል ድምዳሜ ላይ መድረስ አስጋሪ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

የምርጫ ሥነምግባር አዋጁ በተለይም ከሴቶች በተጨማሪም የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ በሚያሳድግ መልኩ ማሻሻያ እንደተደረገበት ቦርዱ ገልጿል፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

19 Jan, 07:56


#እንኳን_አደረሳችሁ!

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ!

#አሐዱ በዓሉ የሠላም፣ የጤና፣ የደስታ የአብሮነት በዓል እንዲሆን ከልብ ይመኛል፡፡

መልካም በዓል!
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

19 Jan, 07:46


የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ ጃንሜዳ በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል

ጥር 11/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የ2017 ዓ.ም. የጥምቀት በዓል ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት፣ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች አምባሳደሮች፣ የክብር እንግዶች ምዕመናንና ምዕመናት እንዲሁም በርካታ የውጪ ሀገራት ጎብኝዎች በተገኙበት በመከበር ላይ ይገኛል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

13 Jan, 17:05


#አሐዱ_አንቀፅ

"ፖለቲካው የኢኮኖሚው ጥርቅም መልክ ነው!"

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/Cz_7vNGSyDc?si=GJzFJKTtN_vEFXTQ

AHADU RADIO FM 94.3

13 Jan, 14:52


የጤፍ እና የእንጀራ ደረጃ ወደ አፍሪካ የደረጃ አውጭ ድርጅት መላኩ እና ስምምነት ላይ መደረሱ ተገለጸ

ጥር 5/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ የሚገኙ ሀገር በቀል ምርቶችን፣ አገልግሎቶችን እና ፈጠራዎችን ለሁሉም እውቅና መስጠት የሚከብድ ቢሆንም፤ በአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጠና ሊሸጡ እና የንግድ ትስስሩ ላይ ሊዘዋወሩ የሚችሉ ምርቶችን ደረጃ የማውጣት ሥራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ለአሐዱ ገልጿል።

"አሁን ላይ የሰዎች አኗኗር ዘይቤ እየተቀየረ ሲሄድ ምርቶችን በደረጃቸው መርጦ የመጠቀም ልምድ እየጨመረ ነው" የተባለ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ምርቶች በደረጃ ልክ ሲዘጋጁ ሁሉም እንደ ምርጫው ገዝቶ እንዲጠቀም እድል የሚሰጥ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር መሰረት በቀለ ለአሐዱ እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ያሉ ምርቶችን ሁሉ ደረጃ ማውጣት ባይቻልም ነገር ግን ከአፍሪካ ደረጃ አውጭ ድርጅት በጤፍ እና በእንጀራ የወጡ ደረጃዎች ላይ ስምምነት ተደርጓል፡፡

"ይህ መሆኑ የንግድ እንቅስቃሴን የሚያሳድግና የምርቶችንም ተፈላጊነት የሚጨምር ነው" ሲሉ አክለዋል።

የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በሀገር ውስጥ ላሉ ምርቶች፣ አገልግሎቶች እና የፈጠራ ሥራዎች ደረጃን ሲያወጣ ላለፉት 50 ዓመታት የቆየ ተቋም እንደመሆኑ፤ እስካሁን የመዘገባቸው የደረጃዎች ብዛት 12 ሺሕ 161 መሆኑ ተገልጿል፡፡

ኢንስቲትዩቱ በሰባት ዋና ዋና ዘርፎች ማለትም፤ በምግብ እና የግብርና ውጤቶች፣ በኤሌክትሮ ቴክኒካል፣ በጤና እንዲሁም በኮንስትራክሽን እና በሲቪል ምህንድስና እንዲሁም በሌሎችም ዘርፎች ያወጣቸው ደረጃች መኖራቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ዶክተር መሰረት በቀለ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

እንዲሁም አስገዳጅ የሆኑ ደረጃዎች መኖራቸውን የገለጹም ሲሆን፤ በየዓመቱ ከሚወጡት ደረጃዎች ተጨማሪ የሚያስፈልግ ከሆነ በሚል ዳሰሳ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

"ተቋሙ ከመዘገባቸው ደረጃዎች ውስጥ አብዛኛውን ቁጥር የሚይዙት ከምግብ እና ግብርና ምርቶች ጋር የተያያዙ ደረጃዎች ናቸው" ሲሉም ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡
ኢንስቲትዩቱ ደረጃዎችን ሲሰጥ የቆይታ ጊዜን እንደሚመለከት የተገለጸ ሲሆን፤ ቀጣይነት የሌለው ምርት ላይ ደረጃ እንደማይወጣ ነው የተነገረው፡፡

በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት የሽሮ ደረጃ ሊወጣ እንደሆነ ተገልጾ የነበረ ሲሆን፤ "አሁን ላይም ይህ ደረጃ ወጥቶ ሥራ ላይ ውሏል" ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ምክር ቤት ባካሄደው 40ኛ እና 41ኛ ጉባኤው 350 ደረጃዎችን ማጽደቁም የሚታወስ ነው፡፡

በእመቤት ሲሳይ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

13 Jan, 14:18


ሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ወደ ማህበረሰቡ ሲያሰራጩ የነበሩ 7 ግለሰቦች ከነኤግዚቢቱ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ

ጥር 5/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ የካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው ማራቶን ሕንጻ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ፤ የተለያዩ ቁሳቁሶችን በመግዛት እና በመሸጥ ሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ወደ ማህበረሰቡ ሲያሰራጩ የነበሩ 7 ግለሰቦች ከነኤግዚቢቱ በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራው መቀጠሉን የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

ፖሊስ በቦታው ቁጥጥር በሚያደርግበት ሰዓት በገበያ ቦታዎች ሁለት ግለሰቦች አትክልት እና ፍራፍሬ ግብይት ሲያደርጉ በመጠራጠር ባደረገው ፍተሻ 14 ሺሕ 600 ሀሰተኛ ብር እንደተገኘባቸው ተገልጿል።

በዚህም መነሻነት ባደረገው ምርመራ የማስፋት ሥራ እና በሌላ አንድ ተጠርጣሪ ላይ በተደረገ አካላዊ ፍተሻ 18 ሺሕ 600 ሀሰተኛ ብር መያዙንም ፖሊስ መምሪያው አስታውቋል።

የወንጀሉን ምንጭ ለማወቅም ፖሊስ ምርመራ የማስፋት ተግባራትን ማከናወኑም የተገለጸ ሲሆን፤ የፍ/ቤት የመበርበሪያ እና የመያዣ ትዕዛዝ በማውጣት በዋና ዋና ተጠርጣሪዎች ላይ ባደረገው ብርበራ በአጠቃላይ 50 ሺሕ 200 ሀሰተኛ ብር እና 7 ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ የማስፋት ሥራ እየሰራ እንደሚገኝ ፖሊስ ገልጿል።

በተጨማሪም የተያዘውን ኤግዚቢት ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሾላ ቅርንጫፍ በመውሰድ ሀሰተኛ መሆኑን የማረጋገጥ ሥራ እንደተሰራ እና እንዲወገድ መደረጉንም ፖሊስ መምሪያው አመላክቷል።

ወደ ፊትም ሕገ ወጥ ተግባራትን እና መሰል ወንጀሎችን የመከላከሉን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የጠቀሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ማህበረሰቡ እንደዚህ ዓይነት አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከት ጥቆማ በመስጠት እና ትብብር የማድረግ የተለመደ ተግባሩን አጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ መልዕክቱን አስተላልፏል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

13 Jan, 13:18


'የፕሪቶሪያው ውል ለመፈፀም ግዴታ የተጣለባቸው አካላት ሊያስፈፅሙ አልቻሉም' በሚል ሀሳብ በዛሬው ዕለት በመቀሌ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ ተካሄደ

ጥር 5/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በመቀሌ ከተማ ሮማናት አደባባይ በተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ፤ 'ይኣክል' ወይንም 'ይበቃል' የሚሉ መፈክሮችን የያዙ በርካታ ሺሕ ሰላማዊ ሰልፈኞች ጥያቄያቸውን ለፕሪቶሪያው ውል ተዋዋዮች አንስተዋል፡፡

ሰላማዊ ሰልፉን ያዘጋጀው "ፅላል ሲቪል ማህበረሰብ ምዕራብ ትግራይ" በሰለፉ ላይ፤ ከ1 ሺሕ 500 እስከ 2 ሺሕ የሚገመት ሕዝብ መሳተፉን ለአሐዱ ገልጿል፡፡

ለአሐዱ ሀሳባቸውን የሰጡት ፅላል አባልና የ'ይአክል' ወይንም 'ይበቃል' ንቅናቄ አስተባባሪ ዳንኤል ነጋሽ፤ የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዲከበር የሚጠይቅ ሰልፍ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ለራሱ ዓላማ ለመጠቀም የሚያስብ አካላቶች እጅ በመውደቁ ከነሱ በማውጣት ለሕዝቡ ጥቅም ላይ እንዲውል አስበው መካሄዱን ተናግረዋል፡፡ አካላት ያሏቸውን ግን ማን እንደሆኑ ከመናገር ተቆጥበዋል፡፡

አቶ ዳንኤል በዛሬው ዕለት የተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በዋነኝነት ከምዕራብ ትግራይ ተፈናቅለው በአቢ አዲ እና በሌሎች መጠለያ ካምፖች የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ የሚጠይቅ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የሰላማዊ ሰልፈኞች ጥያቄ በዋናነት ለተደራዳሪ ወገኖች መሆናቸውን የሚያነሱት አቶ ዳንኤል፤ ጥያቄው በዋናነት ለፌደራል መንግሥት እና ለህወሓት ድርጅት እንዲሁም ይህንን ለማስፈፀም ለተቋቋመው ግዚያዊ አስተዳዳር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በሰልፉ ላይ 'ይበቃል' የሚል ባነር የያዙ እንዲሁም፤ 'ለ1523 ቀናት በፕላስቲክ ቤት መኖር ይብቃን'፣ 'ጦርነት እንጠየፋለን፤ ሰላም እንሻለን'፣ 'ወደ ቀያችን እንመለስ'፣ 'የፖሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ይከበር' እና ሌሎች ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡

ፅላል ሲቪል ማህበረሰብ ምዕራብ ትግራይ በቀጣይ ቀናትም ሰልፉ እንደሚቀጥል የድርጅቱ አባልና የ'ይአክል' ንቅናቄ አስተባባሪ አቶ ዳንኤል ነጋሽ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

13 Jan, 12:58


በስድስት ወራት ውስጥ 1 ሺሕ 165 ሀሰተኛ ደረሰኞች ጥቅም ላይ እንዳይውሉ መደረጉ ተገለጸ

👉በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ከ451 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተሰብስቧል


ጥር 5/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ባለፉት ስድስት ወራት የሕግ ተገዢነትን ለማስፈን በተደረገው ጥረት 1 ሺሕ 165 ሃሰተኛ ደረሰኝ ጥቅም ላይ እንዳይውል መደረጉን የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ገለጹ፡፡

ደረሰኞቹ በ153 ድርጅቶች ጥቅም ላይ ሲውሉ የነበር ሲሆን፤ በዚሁም 1 ቢሊዮን 210 ሚሊዮን 91 ሺሕ 184 ብር ሃሰተኛ ግብይት ለታክስ ዓላማ እንዳይውሉ መደረጉም ተመላክቷል፡፡

"የሕግ ተገዢነትን ለማስፈን የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል" ያሉት ሚኒስትሯ፤ እንዲህ ባለ አላስፈላጊ ሕገ-ወጥ ተግባር ላይ ተሳትፎ የሚያደርጉ አካላትም ከዚህ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል፡፡

በሌላ በኩል በመጀመሪያው ግማሽ ዓመት ከሀገር ውስጥ ታክስ እንዲሁም ከጉምሩክ ቀረጥ እና ታክስ ከ451 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡

ባለፉት ስድስት ወራት በሀገር ውስጥ ታክስ 254 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ፤ 247 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር እንዲሁም፤ ከውጭ ንግድ ቀረጥ እና ታክስ 190 ነጥብ 9 ቢሊዮን ለመሰብሰብ ታቅዶ 203 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር መሰንሰቡን ተናግረዋል፡፡

በድምሩ ከሀገር ውስጥ ታክስ እና ከጉምሩክ ቀረጥና ታክስ 451 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወይም የዕቅዱን 101 በመቶ መሰብሰብ መቻሉን አንስተዋል፡፡

የገቢ አሰባሰቡ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ106 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወይም የ110 በመቶ ብልጫ እንዳለውም መናገራቸውን አሐዱ ከሚኒስቴሩ ያገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

13 Jan, 12:34


በሕገ-ወጥ ደላሎች በመታለል ዜጎች ለከፋ ችግር እየተጋለጡ መሆኑ ተገለጸ

ጥር 5/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ኢትዮጵያዊያን በሕገ-ወጥ ደላሎች 'ወደ ተለያዩ ውጭ ሀገራት እንልካችኋለን' በሚል በተሳሳተ መረጃ ወደ ከፋ ችግር እየገቡ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

በርካታ ዜጎችም በሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ተታልለው እና ከፍተኛ ገንዘብ ከፍለው ከሀገራቸው እየወጡ፤ ለከፍተኛ ችግሮች እየተዳረጉ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

በግንዛቤ እጥረት ምክንያት ዜጎች በሕገ-ወጥ ደላሎች ወደተለያዩ ሀገራት እንደሚሄዱ የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህም በርካቶችን ወደ ሀገራቸዉ እንዲመለሱ የማድረግ ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝም አመላክቷል።

ይሁን እንጂ በተለያየ ሁኔታ ወጣቶችና ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ሕጻናት ለአካላዊ ጥቃት፣ ለረሀብ፣ ለአይምሮ በሽተኛነት እንዲሁም ለተለያ ስነልቦናዊና ማህበራዊ ችግሮች እየተዳረጉ መሆኑ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም ሴቶች እንደሚደፈሩና ከዚህም አልፎ ሕይወታቸዉን እስከማጣት ድረስ ለችግር እየተጋለጡ መሆኑን በሚኒስቴሩ የሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር መከላከል እና የተመላሽ ዜጎች ጉዳይ መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ደረጄ ተግይበሉ ለአሐዱ ተናግረዋል።

መሪ ሥራ አስፈጻሚው አክለውም ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች በመታለል ለተለያዩ ችግሮች እንዳይጋለጡ ማንኛዉም ማህበረሰብ ትብብር ሊያደርግ እንደሚገባ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፤ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ሕገወጥ ደላሎችም ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ለማድረግ ከሚመለከተዉ አካል ጋር በጋራ በመሆን ቁጥጥር እንደሚያደርጉም ገልጸዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በ2012 ዓ.ም በሰው መነገድና ሰውን ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ያለመ አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እንዲወጣ ተደርጎ ወደ ሥራ መገባቱ ይታወቃል።

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 17:30


#አሐዱ_አብይ_ጉዳይ

"ዓለም አቀፍ መልክ እየያዘ የመጣው የመሬት መንቀጥቀጥ!"

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/WFFbhSMqibU?si=lNSjnPCVmfsk4v0u

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 14:22


ሦስት የትግራይ ፓርቲዎች 'ትግራይን የማዳን ቃል-ኪዳን' በሚል ሀሳብ ጥምረት መፍጠራቸውን አስታወቁ

ጥር 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ብሔራዊ ባይቶና አባይ ትግራይ፣ አረና ለዲሞክራሲ ለልዑዓላዊነት እና ውድብ ናፅነት ትግራይ የተሰኙ ሦስት በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች 'ትግራይን የማዳን ቃል-ኪዳን' በሚል ጥምረት መፍጠራቸውን ገልጸዋል፡፡

በአሁን ሰዓት በትግራይ ህልውና ላይ ከፍተኛ የሆኑ አደጋዎች መጋረጡ ለዚህ ጥምረት ምክንት መሆኑን ለአሐዱ የገለጹት፤ የአረና ለዲሞክራሲ ለልዑዓላዊነት ሊቀመንበር አምዶም ገብረስላሴ ናቸው፡፡

ሊቀመንበሩ ለግዜው የፓርቲያቸውን ፕሮግራም ወደ ጎን በመተው በትግራይ ሉዓላዊ ግዛት ማስከበር ላይ፣ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው የሚመለሱበትን እና ጠንካራ ድጋፍ የሚደረግበትን ሁኔታ ላይ በጥምረት ለመስራት ማሰባቸውንም ተናግረዋል፡፡

በትግራይ ያሉ መሠረታዊ ችግሮችንና በአጠቃላይ በአሁን ሰዓት ትግራይ ያለችበት ሁኔታ አስቸጋሪ በመሆኑ ፓርቲዎች ይህንን አደጋ ለመመከት ጥምረት መፍጠራቸውን ተናግረዋል፡፡

አሐዱም "ለመሆኑ ይህ በፓርቲዎች ተፈጠረው ጥምረት ውህድ ፓርቲ እንዲሆኑ ነው ወይስ በምን ምልኩ በጋራ ለመስራት ነው የታሰበው?" ሲል ጠይቋል፡፡

የአረናው ሊቀመንበር አምዶም ገብረስላሴ ይህንን ሲመልሱ፤ በሦስቱ ፓርቲዎች መካከል የተደረገው ጥምረት መሆኑን በማንሳት ጥምረቱም በትልልቅ እና አንድ በሚያደረጉ አጀንዳዎች ላይ በጋራ ለመስራት ታስቦ የተመሰረተ መሆኑን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"የትግራይ ሕዝብ ሳይድን የሚድን ፓርቲ አይኖርም" የሚሉት ደግሞ ባይቶና አባይ ፓርቲ ሊቀመንበር ክብሮም በረኸ ናቸው፡፡

ፓርቲዎቸ ከትንሽ ጉዳይ እስከ ትልቁ ጉዳይ ላይ በጋራ ለመስራት ማሰባቸውን የሚገልጹት ሊቀመንበሩ፤ "በርካታ ልዩነቶች ቢኖሩብንም ለሕዝቡ ይጠቅማል የሚለውን ሁሉንም ነገር እናደርጋለን" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

አሐዱም "ለመሆኑ ይህ ጥምረት በቀጣይ ለሚመጣው 7ኛ ዙር ሀገራዉ ምርጫ ላይ በጋራ እስከመወዳር ድረስ የሚደርስ ጥምረት ነው ወይ?" ሲል ጠይቋል፡፡

አቶ ክብሮም በምላሻቸውም "ምርጫው ትንሹ ነገር ነው" ያሉ ሲሆን፤ ከምርጫ ጀምሮ ማንኛውም ዓይነት ጉዳይ ላይ ጥምረት ፈጥረው እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

በ2015 ዓ.ም ክረመት ወር ላይ 'ሥር ነቀል ለውጥ' በሚል አምስት የሚሆኑ የክልሉ ፓርቲዎች ሰላማዊ ሰልፍ ላመድረግ ጭምር ሞክረው የነበረ ቢሆንም ብዙ ጥፋት ጠፍቶ መክሸፉ ይታወሳል፡፡

ከአሐዱ ጋር ቆይታ ያደረጉት ፓርቲዎችም የጥምረቱ መነሻው ከዛ ጀመረ መሆኑን በመግለጽ፤ በተለይም የፕሪቶሪያው ሰላም ስምምነት እንዲከበር ጥምረቱ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 14:10


በተያዘው ዓመት ለታላቁ ህዳሴ ግድብ 110 ሚሊዮን ብር ለመሰብስ መታቀዱ ተገለጸ

ጥር 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም 96 ነጥብ 6 በመቶ የደረሰ ሲሆን፤ ቀሪውን ሥራ ለማጠናቀቅ ከፋይናንስ ተቋማት ጋር በመሆን በዚህ ዓመት 110 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ መታቀዱ ተገልጿል፡፡

ይህንን የገንዘብ መጠን በተያዘው ዓመት በተለያዩ መንገዶች ለመሰብሰብ መታቀዱን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጽህፈት ቤት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አረጋዊ በርሄ ተናግረዋል፡፡

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ በዚህም ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንድሁም የኢትዮጵያ ወዳጆች አሁንም ተሳትፎቸውን አጠናክረዉ እንዲቀጥሉ የድጋፍ ማሰባሰቢያ ንቅናቄ መጀመሩ ተገልጿል።

ንቅናቄው የህዳሴ ግድብ ቦንድ ገዝተዉ የማያዉቁ አዳዲስ የፋይናንስ ተቋማት የቦንድ ግዥ እንዲፈጽሙ በማድረግ እስከ 60 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብ በማቀድ ተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም ንቅናቄው ከዚህ ቀደም ቦንዱን ገዝተዉ የመመለሻ ጊዜዉ የደረሰ ቦንድ ያላቸዉ ደግሞ፤ በድጋሚ እንዲያድሱ በማድረግ 50 ሚሊዮን ብር ለመሰብሰብና በአጠቃላይ በዚህ ዓመት በድምሩ 1 መቶ 10 ሚሊዮን ብር ገቢ ማድረግን አላማው ያደረገ ነው ተብሏል፡፡

በገቢ ማሰባሰቢያ ንቅንቄው ላይ የ32 ባንኮች፣ የ18 ኢንሹራንሽ ኩባንያዎችና የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ቦርድ ሰብሳቢዎችና ፕሬዝደንቶች ተገኝተዋል፡፡

ይህ ድጋፍ የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም የንቅናቄው ተሳታፊዎች በጋራ እንደሚሰሩ ገለጸዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 12:20


#አሐዱ_መድረክ

"ዲፕሎማቶቻችን ሥራቸው ምንድን ነው?"

አሐዱ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን "የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚያደርገው ትግል" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ያዘጋጀውና፤ የዲፕሎማሲ ባለሙያዎች፣ የፓለቲካ ባለሙያዎች፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ፖለቲከኞች እንዲሁም የሀገር ጉዳይ የሚመለከታቸው አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ (ክፍል አንድ)

ውይይቱን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
https://youtu.be/-thZBNljf2Y?si=Pk9DCMNf0GXL1fHq

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 11:10


በአዲስ አባባ ልዩ የዲያስፖራ ንቅናቄ ወር ሊካሄድ መሆኑ ተገለጸ

ጥር 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በመዲናዋ በተያዘው የጥር ወር ለመጀመሪያ ጊዜ ልዩ የዲያስፖራ ንቅናቄ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ማህበር አስታውቋል።

የዲያስፖራ ሳምንቱ በተለያዩ የዓለም ሀገራት የሚገኘው የኢትዮጵያ ዲያስፖራ በሀገሪቱ በሚከናወን የልማት እንቅስቃሴ በሙሉ የባለቤትነት ስሜት መሳተፋ እንዲችል ለማድረግ የሚካሄድ መሆኑን፤ የማህበሩ ፕሬዝዳንት ቅድስት ልዑልሰገድ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ዲያስፖራው እርስ በርስ እንዲተዋወቅና ከሕዝብና ከመንግሥት ጋር ያለው ግንኙነት የበለጠ የዳበረ ሁኖ ሀገሩን የሚጠቅምበትን መንገድ ለማመቻቸት ያለመ መሆኑን አክለዋል።

የማህበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቃልአብ ግርማ በበኩላቸው፤ "ከልማት፣ መዋዕለ ንዋይን ከማፍሰስና ከሥራ በተጨማሪ በሀገሩ ጉዳይ በቅርበት እንዲሳተፍ ከማስቻል አኳያ ዲያስፖራው ስለሀገሩ ያለው አመለካከትና እውቀት ይበልጥ እንዲጨምር ለማድረግ ነው" ብለዋል።

"የትኛውም ዲያስፖራ ለረዥም ዓመት በውጪ ሀገር ቢያሳልፍም ልቡ ሁሌም ሀገሩ ላይ በመሆኑ፤ ይሄ እንቅስቃሴ ዲያስፖራው የበለጠ ወደ ሀገሩ እንዲመጣና የተለያዩ የልማት ሥራዎች ላይ እንዲሳተፍ ያበረታታል ሲሉ" ገልጸዋል።

በተጨማሪም በወሩ ዲያስፕራው ማህበረሰብ አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎችን የሚጎበኝ ሲሆን፤ የፓናል ውይይት፣ የታሪካዊ ቦታዎች ጉብኝት እና የእግር ጉዞ መርሃ ግብር እንደሚኖርም ተነግሯል፡፡

ይህ የመጀመሪያው የዳያስፖራ ወር እስከ ጥር 30 በተለያዩ መርሃ ግብሮች እንደሚከበር የተገለጸም ሲሆን፤ ንቅናቄው በቶሮንቶ ካናዳም የሚቀጥል መሆኑ ተመላክቷል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 10:44


በአዋሽ ፈንታሌ በተከሰተው የመሬት መሰንጠቅ ምክንያት ከወረዳው ለተፈናቀሉ 7 ሺሕ 500 ሰዎች ድጋፍ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ

ጥር 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በተደጋጋሚ የተከሰተውን ርዕደ መሬት ተከትሎ፤ ከወረዳው ለተፈናቀሉ 7 ሺሕ 500 ሰዎች የፌዴራል አደጋ ስጋትና ሥራ አመራር ኮሚሽን ከክልል፣ ከዞንና ከወረዳ አመራሮች ጋር በመተባበር ድጋፍ እያደረገ እንደሚገኝ የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል፡፡

የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ አስተዳደር አቶ አደም ባሂ ለአሐዱ እንደገለጹት፤ ለተፈናቃዮች የመጠለያና ምግብ ነክ ድጋፎች እንዲሁም ከክልሉ ጤና ቢሮና ከፌደራል ጤና ሚኒሲቴር ጋር በመቀናጀት ጊዜያዊ የሕክምና እርዳታ እንዲያገኙ እየተደረገ ይገኛል፡፡

በተጨማሪም 'የተፈጠረው ችግር የሚቆይበት ጊዜ ስለማይታወቅ ተፈናቃይ ተማሪዎች ትምህርታቸውን ማቆም የለባቸውም' ተብሎ ስለታሰበ፤ ጊዜያዊ የመማሪያ ድንኳን በመትከል የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀመር የተለያዩ የትምህርት መርጃ መሳሪያዎች እየተጓጓዙ መሆኑን ገልጸዋል።

አስተደዳሪው አክለውም፤ ከሰኞ በኋላ የመማር ማስተማር ሥራው እንደሚጀመር ለአሐዱ ተናግረዋል።

በተከሰተው አደጋ ከአጎራባች ክልል ምንም አይነት ድጋፍ እንዳላገኙ የገለጹት አቶ አደም፤ ከዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እና ከፌዴራል መንግሥት ከፍተኛ ድጋፍ እያገኙ መሆኑንም አስታውቀዋል።

አስተዳደሪው በወረዳው ከፍተኛ የመሬት መሰንጠቅ መኖሩን ገልጸው፤ ነዋሪዎች ከአንድ አካባቢ ወደ ሌላ አካባቢ ለመንቀሳቀስ መቸገራቸውን ጠቁመዋል።

በተያያዘም የሰመራ ዩንቨርስቲ የጂኦሎጂ ባለሙያዎች ሂደቱን እየተከታተሉ ሙያዊ ድጋፍ እየሠጡ መሆኑን የተናገሩ ሲሆን፤ " አደጋ ይከሰትባቸዋል ከተባሉ አካባቢዎች ኅብረተሰቡን የማውጣት ሥራ እየተሰራ ነው" ብለዋል፡፡

በክልሉ በተደጋጋሚ እየተከሰተ በሚገኘው ርዕደ መሬት ምክያት ከ58 ሺሕ በላይ ሰዎች ጊዜያዊ መጠለያ ገብተው ሰብዓዊ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን በክልሉ ያቋቋመው ኮማንድ ፖስት አስታውቋል፡፡ በርዕደ መሬቱ ከ100 በላይ ቤቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው የተገለጸ ሲሆን፤ በርካታ እንሰሳቶች መሞታቸውም ተነግሯል፡፡

በተጨማሪም በርዕደ መሬቱ ምክንያት፤ በአዋሽ ፋንታሌ፣ ዱላሳ እና ሓንሩካ ወረዳዎች በሚገኙ 37 ትምህርት ቤቶች ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 16 ትምህርተ ቤቶች ሙሉ በሙሉ ሲወድሙ፤ 21 ትምህርት ቤቶች ደግም ከፊል ጉዳት እንደረሰባቸው የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

በህይወት ጌትነት
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 09:41


በተሽከርካሪ አደጋ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች አስቸኳይ ሕክምና የሚሰጡ ተቋማት የአገልግሎት ክፍያ በመዘግየቱ ቅሬታ እያቀረቡ ነው ተባለ

ጥር 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ በተሽከርካሪ አደጋ የአካል ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች አስቸኳይ ሕክምና እንዲሰጥ የሚያዝዘውን መመርያ ተከትሎ፤ ለሚሰጡት አገልግሎት በፍጥነት ክፍያ ስለማይፈጸምላቸው ቅሬታ እያቀረቡ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

ተቋማቱ የአገልግሎት ክፍያ እየዘገየብን ነው ሲሉ ቅሬታ እንደሚያቀርቡ፤ በፌዴራል መንገድ ደኅንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት የድኅረ ትራፊክ አደጋና መድን አስተዳደር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጫላ ፈይሳ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"በሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ አደጋ የመድን ፖሊሲ የሚከፈለውን የአረቦን ተመን የካሳ መጠን ክፍያ ለመወሰን በሚኒስትሮች ምክር ቤት የወጣው ደንብ ቁጥር 554/2016 የክፍያ መጠኑን ከፍ ያደረገ ቢሆንም፤ የሕክምና ተቋማት እርዳታ ቢሰጡም ክፍያ እንደሚዘገይባቸው እየገለፁ ነው" ሲሉ አክለዋል፡፡

በኢትዮጵያ በትራፊክ አደጋ ተጎጂዎች እና ለተጎጂ ቤተሰቦች ሲሠጥ የቆየው የካሳ መጠን መሻሻሉን የትራንስፖርትና ሎጀስቲክ ሚኒስቴር በቅርቡ ይፈ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

በተሻሻለው ደንብ በተሽከርካሪ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች ለአስቸኳይ ሕክምና ይከፈል የነበረውን 2 ሺሕ ብር ወደ 15 ሺሕ ብር እንዲሁም፤ ለሞት አደጋ ይከፈል የነበረውን የ40 ሺሕ ብር ካሳ መጠን ወደ 250 ሺሕ ብር ከፍ እንዲደረግ መወሰኑ የሚታወስ ነው፡፡

በዳግም ተገኝ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 08:57


ከ41 ባቡሮች ውስጥ እየሠሩ ያሉት 16ቱ ብቻ መሆናቸውን ተገለጸ

ጥር 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ካሉት 41 ባቡሮች እየሠሩ ያሉት 16ቱ ብቻ እንደሆኑ አስታውቋል፡፡

የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ብርሀን አበባው ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ወደ ሥራ ሲገባ 41 ባቡሮች የነበሩት ቢሆንም አሁን አገልግሎት እየተሰጡ ያሉት ባቡሮች ቁጥር 16 ብቻ ነው፡፡

ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ባቡሮች አገልግሎት የማይሰጡት በብልሽት ምክንያት መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።

ባቡሮቹ ብልሽት በሚያጋጥማቸው ጊዜ የጥገና ዕቃዎች ገበያ ላይ የሉም ያሉት ኃላፊው፤ ችግሩን ለመፍታት ከአንዱ ባቡር እየተነቀለ ወደ ሌላኛው ሲገጠም መቆየቱ ተናግረዋል።

የባቡሮቹን ሶፍትዌር ለመጠቀም ፍቃድ አለመኖሩም ለባቡሮቹ መቆም ዋነኛው ምክንያት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ተበላሽተው የቆሙ ባቡሮችን ወደ ሥራ ለማስገባት፣ የተሻለ የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት እና ዘርፉ አሁን ካለበት የውጤት መቀዛቀዝ ለማውጣት የሪፎርም ሥራዎች መጀመራቸውን አብራርተዋል፡፡

በዚህም መሰረት የቆሙ ባቡሮችን ወደ ሥራ ማስገባት በሚሰራው ሥራለ፤ እስከ መጪው ሰኔ ድረስ አምስት ባቡሮች ወደሥራ እንዲገቡ እንደሚደረግ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ጊዜም የሁለት ባቡሮች የጥገና ሥራ መጠናቀቁን ጠቁመው፤ እነኝህ ባቡሮች በቀጣይ ሦስት ቀናት ወደ ሥራ እንደሚገቡ አብራርተዋል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

11 Jan, 08:16


በጎንደር ከተማ በ672 ሚሊየን ብር የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትና የቤተ-እስራኤላውያን ሙዚየም ሊገነባ ነው

ጥር 3/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ Stragle to save Ethiopian Jewary የተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት፤ በ672 ሚሊየን ብር ወጪ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤትና የቤተ-እስራኤላውያን ሙዚየም ሊገነባ መሆኑ ተገልጿል።

የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው ድርጅቱ በተገለጸው ወጪ በከተማዋ የማህበራዊ ተቋማትን ለመገንባት መስማማቱን ገልጸዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ ለሁለቱ ማህበራዊ ተቋማት ግንባታ የሚውል 50 ሺሕ ካሬ ሜትር መሬት የመስሪያ ቦታ ለመስጠት መዘጋጀቱን ተናግረዋል፡፡

በስምምነት ስነ-ስርዓቱ ላይም በድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ሚስተር ጆ ፋይት ተገኝተዋል፡፡

ለማህበራዊ ተቋማቱ የግንባታ የገንዘብ ድጋፍ የተገኘው የአሜሪካን ጅውሽ ማህበረሰብ ከተባለ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት መሆኑ በስምምነቱ ላይ መመላከቱን ከክልሉ ኮምዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Jan, 16:18


በላሊበላ ከተማ በተከበረው የገና በዓል ላይ ከ888 ሺሕ በላይ ሰዎች መገኘታቸው ተገለጸ

ታሕሳስ 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በዘንድሮው ዓመት በላሊበላ ከተማ በተከበረው የገና በዓል ላይ፤ ከ888 ሺሕ በላይ ሰዎች መገኘታቸውንና በዓሉ ያለ ምንም የፀጥታ ችግር ተከብሮ በሰላም መጠናቀቁን የሰሜን ወሎ ዞን ባህልና ቱሪዝም መምሪያ አስታውቋል።

የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል አስመልክቶ በከተማዋ በተከበረው በዚህ በዓል ላይ፤ ከ495 በላይ የውጪ ሀገራት ጎብኚዎች መሳተፋቸውንም የመምሪያው ኃላፊ ገነት ሙሉጌታ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

የአካባቢው ማኅበረሰብ በዓሉን ለማክበር ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲሁም ከውጪ ሀገራት የመጡ ታዳሚዎችን በመቀበል እግር አጥቦ ማስተናገዱን የገለጹት ኃላፊዋ፤ ከበዓሉ መጠናቀቅ በኋላም በሬ አርዶ አብልቶና አጠጥቶ መሸኘቱን አክለው ገልጸዋል።

"የዚህኛው ዓመት የገና በዓል አከባበር እንከንየለሽ ነበር" የሚሉት ኃላፊዋ፤ የተረጋጋ ከነበረው የሰላምና ፀጥታ ባሻገር ምንም አይነት የትራፊክ አደጋ አለመከሰቱን አንስተዋል።

ከታሕሳስ 26 እስከ 28 ባሉት ቀናት ከ17 በላይ በረራዎች ወደ ከተማዋ መካሄዳቸውም ጨምረው ገልጸዋል።

"በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተቀዛቅዞ የነበረው የከተማዋ የቱሪዝም እንቅስቃሴ አሁንም በክልሉ ባለው ግጭት ሳቢያ በእጅጉ እንደተጎዳ ነው" ያሉት ኃላፊዋ፤ ሰላም ለቱሪዝም እድገት ወሳኝ እንደመሆኑ ዘርፉ ብዙ ችግሮች እንዳጋጠሙት አስረድተዋል።

በመሆኑም በዘንድሮው ዓመት የተከበረው የገና በዓል ከሰሜኑ ጦርነት በኋላ ካሉ ዓመታት ጋር ሲነፃፀር፤ የተሻለና ቱሪዝሙን ማነቃቃት የሚችል ጥሩ የሚባል ፍሰት የታየበት እንደነበር ገልጸዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Jan, 14:22


ምክር ቤቱ በነገው ዕለት የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት ለመደንገግ የተዘጋጀውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ያጸድቃል

👉 የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ያጸድቃል ተብሎም ይጠበቃል


ታሕሳስ 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) 6ኛው ዙር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔ በነገው ዕለት ያካሂዳል።

በዚህም መደበኛ ጉባዔው፤ የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ሥርዓት ለመደንገግ በተዘጋጀውን ረቂቅ አዋጅ ላይ የንግድና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ እንደሚያጸድቅ ተገልጿል።

በተጨማሪም የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በሕግና ፍትህና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚቀርበውን ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ መርምሮ ያጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Jan, 13:55


በአማራ ክልል ፕሮጀክቶች ያለ ጨረታ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች ብቻ እየተሰጡ ነው ተባለ

ታሕሳስ 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአማራ ክልል ያሉ የተለያዩ ፕሮጀክቶች ያለ ጨረታ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች እየተሰጡ፤ የግሉ ዘርፍ ከሥራ እንዲወጣ እየተደረገ ነው ሲል የክልሉ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማህበር ገልጿል።

የአማራ ክልል ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማህበር ፕሬዝደንት አቶ ሙሉቀን ቢተው "በክልሉ የሚተገበሩ የተለያዩ ፕሮጀክቶች 'ጨረታ አልወጣም' እንዳይባል ብቻ አምስት ያክል የመንግሥት ባለድርሻዎችን አሳትፈው፤ መልሰው የሚወስዱት የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ናቸው" ሲሉ ለአሐዱ የገለጹ ሲሆን፤ ይህም ተግባር የግሉን ዘርፍ ይበልጥ እያዳከመው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በዚህም የተነሳ ከ6 ሺሕ በላይ ኮንትራክተሮች ችግር ውስጥ መሆናቸው በማንሳት፤ በክልሉ የሚንቀሳቀሱና በኮንስትራክሽን ዘርፉ ላይ የተሰማሩ አካላት ሥራቸውን መስራት እስካለመቻል የደረሱ ችግሮችን እያስተናገዱ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

"ችግሩ ከፍተኛ በመሆኑ በተለይም ያለው የሥራ ሁኔታ በቀዘቀዘበት እንዲሁም ፕሮጀክቶች ያለምንም ጨረታ ለመንግሥት የልማት ድርጅቶች በሚሰጥበት ሁኔታ ውስጥ ኮንትራክተሮች ከፍተኛ ችግር ላይ እየወደቁ ነው" ያሉት የማህበሩ ፕሬዝዳንት፤ በዚህም የተነሳ በርካቶች ቤታቸውን፣ ማሽኖቻቸውን፣ መኪኖቻቸውንና ሌሎች ንብረቶቻቸውን ለመሸጥ እየተገደዱ መሆኑን አስረድተዋል።

በክልሉ በአጠቃላይ ከ6 ሺሕ በላይ የዘርፉ ባለሙያዎች ቢኖሩም በማህበሩ ሥር የታቀፉት 755 አካባቢ ብቻ መሆናቸውን የገለጹም ሲሆን፤ ከእነዚህ ውስጥ ወርሃዊ መዋጮ መክፈል የማይችሉበት ደረጃ ላይ የደረሱ አባላት ስለመኖራቸውም ተናግረዋል፡፡

የለመዱንት ሥራ ትቶ ወደ ሌሎች ዘርፎች መሰማራት ፈታኝ መሆኑን ያነሱት አቶ ሙሉቀን፤ "ይህን ዘርፍ ትተው ሌላ ሥራ ላይ ቢሰማሩ ውጤታማ ላይሆኑ የሚችሉ ባለሙያዎችም አሉ፤ ስለዚህም ጉዳዩ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል" ሲሉ አሳስበዋል፡፡   

አሐዱም "የአማራ ክልል ብቻ ሳይሆን በሌሎችም አካባቢዎች ያሉ እንዲህ አይነት ችግሮችን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በምን መልኩ ነው የሚቆጣረው? እንዲሁም የፌደራል መንግሥቱ ሳያውቅ የአካባቢው እና የክልል ኃላፊዎች እንዲህ አይነቱን ተግባር እንዳይፈፅሙ ምን ድርሻ አላቸው?" ሲል የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ የትምጌታ አስራትን ጠይቋል።

ሚኒስትር ዴኤታው በሰጡት ምላሽ፤ "አስቸኳይ እና በልዩነት የመንግሥት የልማት ድርጅቶት እንዲገቡባቸው የሚያስፈልጉ ቦታዎች ካልሆኑ በስተቀር፤ በሌሎቹ ፕሮጀክቶች ላይ ሁሉም በጨረታ እንዲሳተፉ ይደረጋል" ሲሉ ተናግረዋል።

እሳቸው ይህን ይበሉ እንጂ፤ የአማራ ኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማህበር፤ ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ችግሩን መግለጹን፣ ነገር ግን እስካሁን የመፍትሄ አለማግኘቱን አስታውቋል።

በእመቤት ሲሳይ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Jan, 12:02


በሸገር ከተማ በአንድ ወር ውስጥ ብቻ ከ54 ሺሕ በላይ አሽከርካሪዎች ላይ እርምጃዎች መወሰዱ ተገለጸ

ታሕሳስ 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሸገር ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ የተቀመጠውን ደምብ በተላለፉ ከ54 ሺሕ በላይ አሽከርካሪዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃዎችን መውሰዱን ለአሐዱ አስታውቋል።

በመንገድ ትራንስፖርት ትራፊክ አደጋ ምክንያት በዜጎች ላይ ሚደርሰውን የሞት፣ የአካል ጉዳት እና የንብረት ውድመት ለመቀነስ እና ሕገወጥ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ህብረተሰቡን ለአላስፈላጊ እንግልት የሚዳርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ቁጥጥር እየተደረገ እንደሚገኝ የከተማዋ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ያሲን አህመድ ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለውም "ለትራፊክ አደጋ መከሰት የአሽከርካሪዎች ሥነምግባር ችግር እና የተሽከርካሪ የቴክኒክ ምርመራ ጉድለት ጉልህ ድርሻን ይይዛል" ብለዋል።

በእነዚህ የትራፊክ አደጋ መንሰዔዎች ላይ በተጠና እና በተጠናከረ መልኩ ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅትና በትኩረት ቢሰራባቸውም እስካሁን ችግሩን መቅረፍ አለመቻሉን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ጠጥቶ ከመጠን በላይ በፍጥነት ማሽከርከር ሌላኛው መንስኤ መሆኑን ያነሱ ሲሆን፤ የችግሩን አሳሳቢነት በመረዳት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የዜጎች በሰላም ወጥቶ መግባት ያሳስበኛል፣ ይመለከተኛል የሚል ማንኛውም አካል የትራፊክ አደጋን ተቀዳሚ አጀንዳ እንዲያደርገውም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በወልደሐዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Jan, 11:40


የተፈጠሩ ችግሮችን መፍታት ብቻ ሳይሆን መንስኤው ላይ ትኩረት ተደርጎ ሊሰራ ይገባ ተባለ

ታሕሳስ 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለሚፈጠሩ ችግሮች  መፍትሔ መስጠት ብቻ ሳይሆን፤ የግጭቱ  መንስኤ ላይ ትኩረት ተደርጎ ሊሰራበት ይገባል ሲል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ምክር ቤት አስታውቋል።

የምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት አቶ አህመድ ሁሴን፤ በኢትዮጵያ በአንዳንድ ቦታዎች ላይ የሚስተዋሉ ግጭቶች ለተለያዩ ችግሮች እያጋለጠ መሆኑን አንስተው፤ "መንግሥት ሰፊ የሆነ የሰላም ውይይት መድረኮችን በማዘጋጀት ሊሰራ ይገባል" ብለዋል።


አክለውም በየጊዜው ለሚፈጠሩ ግጭቶች እና አለመግባባቶችን መፍታት ብቻ  ዘላቂ ሰላም እንደማያመጣ ገልጸው፤ "የችግሩ መንስኤ የሆኑ ጉዳዮች ላይ በትኩረት ሊሰራ ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል።

እንዲሁም ሀገራዊ ውይይቶች ስለስላም የሚሰብኩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በማድረግ፤ በሁሉም ማህበረሰብ እኩል ተቀባይነት ያላቸውን ጉዳዮች በመለየት የአስተሳሰብ ለውጥ እንዲኖር ማድረግ እንደሚቻል አንስተዋል።

"በአሁኑ ሰዓት እየተካሄደ ያለው ጥረት የሚፈጠሩ ችግሮችን መፍታት እንጂ መንስኤዎቹ ላይ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራ ባለመሆኑ ለውጥ እየታየ አይደለም" ብለዋል።

በዚህም መሠረት የችግሩ መንስኤ ላይ በሰፊው መሰራት እንደሚገባ አንስተው ያለውን እውቀት፣ ጊዜ፣ ሀብት እና ጉልበት ፈሰስ በማድረግ ሰላም በሚያመጡ ውይይቶች ላይ መሰራ እንደሚገባ አቶ  አህመድ  ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ እየተስተዋለ ያለውን ግጭት ለመፍታ ያደጉ ሀገራትን ተሞክሮ በመውሰድ "ሰላም እንዴት ማምጣት ይቻላል" የሚሉትን ጉዳዮች መመልከት እንደሚገባ ያነሱት ፕሬዝዳንቱ ከችግሩ ይልቅ  መንስኤው ላይ ትኩረት ሊሰጥ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Jan, 10:18


ዳግም ምዝገባ ባላካሄዱ 84 የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

ታሕሳስ 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ዳግም ምዝገባ እንዲያካሄዱ ጥሪ ቀርቦላቸው ምዝገባ ባላካሄዱ 84 የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ርምጃ መውሰዱን አስታውቋል፡፡

የባለስልጣኑ የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ማርታ አድማሱ፤ ወጥነት ያለው የፈቃድ አሰጣጥ ስርዓት እንዲተገበር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ዳግም ምዝገባ እየተከናወነ መሆኑን ለኤፍ ኤም ሲተናግረዋል

በዳግም ምዝገባውም የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማቱ የተሳሳተ ሰነድ ካላቸው እንዲያስተካክሉ አልያም የጎደለውን እንዲያሟሉ እድል ተሰጥቷቸው እንደነበርም ተናግረዋል

ዳግም ምዝገባ እንዲያደርጉ ጥሪ ከቀረበላቸው 102 ተቋማት ውስጥም 84 የሚሆኑት ዳግም ምዝገባ አለማድረጋቸውን ገልጸው፤ "ምዝገባ ያላከናወነ ተቋም በራሱ ፈቃድ ከመማር ማስተማር ሥራው እንደወጣ ይቆጠራል" ብለዋል።

እነዚህ ተቋማትም ከመማር ማስተማር ሥራው ሲወጡ የመውጫ ፎርም እንዲሞሉ የሁለት ሳምንት ጊዜ ገደብ እንደተሰጣቸውም የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚዋ አስታውቀዋል።

አሁን ላይ አምስት ተቋማት ብቻ ይህንን ሂደት የጀመሩ ሲሆን፤ ወደዚህ ሥራ ያልገቡ ቀሪ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደግሞ በፍታብሄር እና በወንጀል ሕግ ተጠያቂ እንደሚሆኑ ተናግረዋል፡፡

ተቋማቱ ከዚህ በኋላ በሰነድ የታገዘ ምዝገባ እንደማያደርጉ እና ዳግም ወደ መማር ማስተማር ሥራው እንደማይመለሱም አረጋግጠዋል፡፡

በቀጣይም ዘጠኝ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ተመሳሳይ ርምጃ እንደሚወሰድ ገልጸው፤ በተቋማቱ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ተማሪዎች አስፈላጊውን መረጃ በማሟላት እስከ ጥር ወር 2017ዓ.ም መጀመሪያ ድረስ ፈቃድ ወዳላቸው ተቋማት እንዲያዛውሩ ትዕዛዝ መሰጠቱንም አስረድተዋል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 15:33


በአፋር እና ኦሮሚያ ክልሎች ለርዕደ-መሬት ተጋላጭ የሆኑ ዜጎች ከስጋቱ ቀጠና ወደ ሌላ ስፈራ የማዘዋወር ሥራ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

👉 እስከ አሁን ለ70 ሺሕ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሆን ሰብዓዊ ድጋፍ መደረጉ ተነግሯል

ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ እና ዱለቻ ወረዳዎች እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ የርዕደ መሬት ክስተት የተፈጥሮ የቅድመ ማስጠንቀቂያ ደወለን ተከትሎ፤ መንግሥት የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

ኮሚሽኑ በክልሎቹ እየተከሰተ ባለው የርዕደ-መሬት ክስተት ሁኔታና ምላሽን አስመልክቶ መግለጫ ያወጣ ሲሆን፤ በእስካሁኑ ሁኔታና ምላሽ እየታየ ያለው ሥራ አመርቂ መሆኑን ገልጿል።

በዚህም መሠረት በአፋር ክልል ሁለት ወረዳዎች ማለትም አዋሽ ፈንታሌና ዱለቻ (ዱለሳ) ወረዳዎች ለችግሩ ተጋላጭ መሆናቸው ተመላክቷል።

በሁለቱም ወረዳዎች ማለትም በአዋሽ ፈንታሌ 6 ተጋላጭ ቀበሌዎች 15 ሺሕ ነዋሪዎች ተጋላጭ ሲሆኑ፤ እስከ አሁን 7 ሺሕ ወገኖች ከስጋቱ ቀጠና ወደ ሌላ ስፈራ መጓጓዛቸው ተገልጿል፡፡

በዱለቻ ወረዳ ደግሞ 20 ሺሕ የሚሆኑ የ2 ቀበሌዎች ወገኖች ተጋላጭ ሲሆኑ፤ ከእነዚህ ቀበሌዎች እስከ አሁን 6 ሺሕ 223 ሕዝብ አካባቢውን መልቀቃቸው ተነግሯል፡፡

በኦሮሚያ ክልል ፈንታሌ ወረዳ የ5 ቀበሌዎች ወገኖች ለአደጋው ተጋላጭ ናቸው ተብሏል።

በ5ቱም ቀበሌዎች 16 ሺሕ 182 ሕዝብ ተጋላጭ ሲሆን፤ እስከ አሁን ድረስ 7 ሺሕ 350 ሕዝብ ከተጋላጨ ስፍራ መውጣታቸው ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም 8 ሺሕ 832 የሚሆኑት ቀሪዎቹ ሰዎች ደግሞ፤ በሚቀጥሉት ቀናት ውስጥ ከስፍራው እንዲንቀሳቀሱ እየተሠራ እንደሚገኝ ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡

ክስተቱን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና ከሌሎች የሚመለከታቸው ተቋማት የተውጣጡ የሳይንቲፊክ ኮሚቴ፣ ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ ሲሆን፤ መገለጽ ያለበትን ቅድመ-ጥንቃቄዎች አስመልከቶ አስፈላጊው መረጃ ለሕዝብ በተከታታይ እንደሚቀርብ አስታውቋል፡፡

ይህንንም ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ማህበራዊ ሚዲያዎችና ድህረ ገጽ መከታተል ይቻላል ተብሏል፡፡

የርዕደ መሬት ንዝረቱ ባለበት አካባቢ ያለ ማህበረሰብ ከንዝረቱ በፊት፣ በንዝረቱ ወቅትና ከንዝረቱ በኋላ ያለውን መወሰድ ያለባቸው ጥንቃቄ እንዲወስዱ አስፈላጊው መረጃ እየተሰጠ እንደሚገኝም ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡

በተጨማሪም ሰብዓዊ ድጋፍን በተመለከተ እስከ አሁን ለ70 ሺሕ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚሆን 1 ሺሕ 550 ኩንታል ምግብ-ነክ እና ለ7 ሺሕ አባወራ የሚሆን ምግብ-ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ወደ ስፍራው መላኩ ተገልጿል፡፡

ይህም በገንዘብ ሲተመን ለምግብ 216 ሚሊዮን 562 ሺሕ 500 ብር እና ምግብ-ነክ ላልሆኑ ቁሳቁሶች 65 ሺሕ 625 ሺሕ ብር በድምሩ 281 ሚሊዮን 562 ሺሕ 500 ብር የሚገመት መሆኑ ተነግሯል፡፡

በኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን በኩል የርዕደ መሬቱን ባህሪያትና የሚጠይቀውን የጥንቃቄ መልዕክቶች በተከታታይ እንደሚያቀርብ የገለጸ ሲሆን፤ በተረጋጋና በሰከነ ሁኔታ አደጋውን ለመሻገር ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትኩረትና በንቃት እንዲንቀሳቀሱ አሳስቧል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 14:59


ሕዝበ ሙስሊሙ ከነገ እሁድ ታሕሳስ 27/2017 ጀምሮ እስከ ጥር 2/2017 ድረስ የሚቆይ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ

ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዩች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤት፤ ከነገ እሁድ ታሕሳስ 27/2017 ጀምሮ እስከ ጥር 2/2017 ድረስ የሚቆይ "ልዩ የሆነ ወደ አላህ የመመለስና መልካም ሥራዎች እየሰሩ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲደረግ" ጥሪ አቅርቧል።

የዑለማ ጉባዔ ጽ/ቤቱ ለጠቅላላው ሕዝበ ሙስሊም ባስተላለፈው መልዕክት፤ "ሀገራችን ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ሰው ሰራሽን በተፈጥሮ ችግሮች ምክንቶች እየታመሰች ትገኛለች።" ብሏል።

"ለዚህም ዋና ምክንያቱ የሰው ልጆች የርስ በስርስ ፍቅር መጥፋት፤ ጥላቻ መስፋፋት የእርስ በርስ መገዳደል መበራከትና የሰው ልጅ ነብስ ከምን ጊዜውም በላይ ርካሽ የሆነበትና በቀላሉ ሕይወት የተቀጠፈ የሚገኝበት ደረጃ ላይ ደርሰናል፡፡" ሲልም ገልጿል።

"ይህ በእንዲህ እንዳለ ከጥፋቶቻችንና ከስህተቶቻችን ለመመለስ ባለመቻላችን ምክንያት ተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመከሰት ላይ ይገኛሉ፡፡" ያለው ጽ/ቤቱ፤ ለአብነት ያህልም ባለፈው ክረምት በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በሲዳማ፤ እንዲሁም በአማራ ክልሎች በተከስተው የመሬት መንሸራተት በርካታ ሰዎች መሞታቸውና ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸውን አንስቷል።

በአሁኑ ወቅት ደግሞ የመሬት መንቀጥቀጥ በተደጋጋሚ በሀገሪቱ እየተከሰተ እንደሚገኝ በመግለጽ፤ "ይህ ሁሉ ክስተት እኛ የሰው ልጆች በምንሰራቸው ወንጀሎች ሳቢያ የሚመጡ ክስተቶች በመሆናችው ነው" ብሏል።

በዚህም ምክንያት ከፊታችን እሁድ ታሕሳስ 27 ቀን2017 ጀምሮ እስከ ጥር 2 ቀን 2017 ድረስ የሚቆይ ልዩ የሆነ ወደ አላህ የመመለስና መልካም ሥራዎች እየሰሩ ለሀገር ሰላምና ደህንነት ዱዓ የማድረግ ቀን ተግባራዊ እንዲደረግ የኡለማ ጉባዔ ጽ/ቤት ለመላው ሕዝበ-ሙስሊም የሚከተሉትን መልእክቶች አስተላልፏል፡፡

በዚህ መሰረት ፦

1. ሕዝበ-ሙስሊሙ በአጠቃላይ ተውበት በማድገረግ ወደ አላህ እንዲመለስ

2. ሁላችንም እርስ በርስ ይቅርታ እንድንባባል፤

3. ለተቸገሩትና ረዳት ለሌላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ሶደቃ ( ምጽዋት) መስጠት

4. በሀገሪቱ ውስጥ በሚገኙ አጠቃላይ መስጂዶች በየአምስት አውቃት ሶላቶች ላይ ቁነት እንዲደረግ፤

5. የቀጣዩ ጁሙአ ቀን በሁሉም መስጂዶች የሚደረጉ ኹጥባዎች በዚህ ዙሪያ እንዲሆኑና አጠቃላይ ዱዓ እንዲደረግ አሳስቧል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 14:05


በጎንደር ከተማ ተጥሎ የነበረው የሰዓት ገደብ እንቃስቃሴ ላይ ማሻሻያ መደረጉ ተገለጸ

ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ ተጥሎ የነበረው የሰዓት ገደብ እንቃስቃሴ ላይ ማሻሻያ መደረጉን የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል።

በከተማው የነበረው የፀጥታ ችግር መሻሻል ማሳየቱን ተከትሎ፤ የከተማው የፀጥታ ም/ቤት በተሽከርካሪና በሰው እንቅስቃሴ ላይ ጥሎት የነበረውን የሰዓት ገደብ ማሻሻሉን ተገልጿል።

የጎንደር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ረ/ኮሚሽነር አየልኝ ታክሎ እንዳሉት፤ የከተማው የፀጥታ ም/ቤት በተሽከርካሪና በሰው እንቅስቃሴ ላይ ጥሎት የነበረውን የሰዓት ገደብ ወደ አራት ሰዓት ከፍ እንዲል ውሳኔ አሳልፏል።

የተፈቀደላቸው ባጃጆች እስከ ምሽት አራት ሰዓት መስራት እንደሚችሉ የገለጹት ረዳት ኮሚሽነሩ፤ ሌሎች ባጆጆች ደግሞ በቀደመው የሰዓት ገደብ እስከ 12 ስዓት ብቻ መንቀሳቀስ እንደሚችሉ ገልጸዋል።

ከተማዋ የገናና የጥምቀት በዓልን በድምቀት እንድታከበር አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ጠቁመው፤ የከተማው ነዋሪም ሆነ እንግዶች በነፃነት መንቀሳቀስ እንዲችሉ ታስቦ የሰዓት ማሻሻያ መደረጉን አስረድተዋል፡፡

በከተማዋ በሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች መስታወት ላይ ጥቁር ስቲከር የለጠፉ ሁሉ እንዲያነሱ ውሳኔ መተላለፉም ተናግረዋል፡፡

ይህን በማያደርጉ አካላት ላይ የፀጥታ ሃይሉ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ ነው አጽንኦት የሰጡት፡፡

የሰዓት ማሻሻያ ገደቡ ከነገ ጀምሮ ተግባራዊ የሚደረግ ሲሆን፤ ሁሉም የተጣለውን የሰዓት ገደብ እንቅስቃሴ አክብሮ እንዲንቀሳቀስ ኮሚሽነሩ ማሳሰባቸውን ከከተማ አስተዳደሩ ኮምዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል ።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 13:48


አካል ጉዳተኞች መብታቸውን ሲጠይቁ እንደተረጂ ተደርገው መታየታቸው ለከፍተኛ ተጽዕኖ እያጋለጣቸው ነው ተባለ

ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አካል ጉዳተኞች በመንግሥትም ይሁን በግለሰብ ደረጃ ያለው አመለካከት እንደ ተረጂ እንጂ ባለመብት ተደርገው እየታዩ ባለመሆኑ፤ እኩል የሆነ ተሳትፎ እንዳይኖራቸው አድርጓል ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አስታውቋል።

በኮሚሽኑ የሴቶች፣ ሕጻናት፣ አካል ጉዳተኞችና አረጋዊያን መብቶች ኮሚሽነር እርግበ ገብረሃዋሪያ፤ "በዓለም አቀፍ ደረጃ የጸደቀውን የአካል ጉዳተኞች መብት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ ቢሆንም፤ በተሳሳተ አመለካከት ምክንያት እኩል የሆነ ተሳትፎ እንዳይኖራቸው ተፅእኖ አሳድረዋል" ሲሉ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

አክለውም "በፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እንድሁም ማህበራዊ እንቅስቀሴ ላይ እኩል የሆነ ተሳትፎ  እንዲኖራቸው መመሪያ ቢደነገግም ተግባራዊ እየሆነ አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኮሚሽኑ በተለያዩ ቦታዎች አካል ጉዳተኞች መብታቸው እንዲጠበቅና በሁሉም ዘርፎች ተጠቃሚነታቸው እንዲረጋገጥ በሚያደርገው ክትትል መሰረት፤ በተሳሳተ አመለካከት ችግር የሚጠይቁት ነገር መብታቸው ሆኖ እያለ እንደ ተረጂ ተደርገው የሚቆጠሩበት ሁኔታ መኖሩን ጠቁመዋል፡፡

ይህንን ችግር ለመፍታት ከሚመለከተው አካል በጋራ በመሆን እየሰሩ እንደሆነ አንስተው፤ ለማህበረሰቡም የግንዛቤ ትምህርቶችን በሰፊው መስጠት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

በማህበረሰቡ ዘንድ ያለው የአመለካከት ችግር በዕለት ተእለት ሥራቸው ላይ ተግዳሮት እንደሆነ ወ/ሮ እርግበ ገብረሐዋርያ ገልጸዋል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ የጸደቀውን መብት ተግባራዊ ለማድረግ እንዲሁም በሁሉም የሥራ ዘርፎች ላይ ተጠቃሚ እንድሆኑ ከሚመለከተው አካል በጋራ በመሆን እየተሰራ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 11:52


በሕገ-ወጥ የእንስሳት እርድ ምክንያት በዓመት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚታጣ ተገለጸ

👉 በመጪው የገና በዓል ለሚከናወኑ የእንስሳት እርዶች አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁ ተነግሯል


ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከሦስት ዓመት በፊት በተጠና ጥናት መሠረት በኢትዮጵያ በሚከናወኑ ሕገ-ወጥ እርዶች ምክንያት በዓመት ከ1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ እንደሚታጣ የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል ለአሐዱ ተናግረዋል።

ኃላፊው እንደገለጹት ድርጅቱ በዋናነት ሕገ-ወጥ እርድ ምክንያት በዜጎች ላይ የጤና፣ የኢኮኖሚና መሰል ችግሮችን የሚያስከትል በመሆኑ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ይገኛል፡፡

ከዚህ ቀደም ከነበረው ሕገ-ወጥ የእርድ አገልግሎት አንጻር ለውጦች መኖቸውን የገለጹት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው፤ ነገር ግን አሁንም በተለያዩ አካባቢዎች በሕገወጥ መንገድ የሚደረግ የእንስሳት እርድ መኖሩን ተናግረዋል፡፡

የቆዳ እና ሌጦ ውጦቶችን ጥራት እና ደህንነት ለማስጠበቅ ሕገወጥ የእንስሳት እርድን ማስወገድ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በዚህም መሠረት የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለመጪው የገና በዓል 3 ሺሕ የቀንድ ከብት እንዲሁም ከአንድ ሺሕ ፍየልና በግ በላይ ለእርድ ማዘጋጀቱን የገለጹት ኃላፊው፤ ለበዓሉ የሰው ኃይል እጥረት እንዳያጋጥም ከ1 ሺሕ 100 በላይ ጊዜያዊ ሠራተኞች መቀጠራቸውን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ለኅብረተሰቡ ንፅህናውን የጠበቀ የእርድ አገልግሎት በፍጥነት እና በቅልጥፍና ለማቅረብ የእርድ መሳሪያዎች እንዲሁም 45 የድርጅቱ የስጋ መጓጓዣ ተሽከርካሪዎች መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል፡፡

በመሆኑም የጥራት ጉድለት ክፍተቶችን ለመፍታት ሕገ-ወጥ የእርድ አገልግሎትን ማስወድ እንደሚገባ አንስተዋል።

በበዓሉ ወቅት ሊያጋጥም የሚችል ሕገ-ወጥ የእንስሳት እርድን ለመቆጣጠር ከአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባስልጣንና፣ ከአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደር ግብርና ኮሚሽን ጋር በጋራ እየተሰራ እንደሚገኝ ኃላፊው ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በእሌኒ ግዛቸው
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 10:06


#አሐዱ_አብይ_ጉዳይ

"ለስድብ ባለቤቶች ወደ ኪሳችን አንግባ"

ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/_lO0j_K49OM?si=on8PRX-ZB6U_bWcG

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 09:04


የተሽከርካሪ ማቆሚያ ቦታን ለሌላ አላማ አውለው የተገኙ 187 የሕንፃ ባለቤቶች 100 ሺሕ ብር መቀጣታቸው ተገለጸ

ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት ውስጥ ብቻ የተሽከርካሪ ማቆሚያ ቦታን ሙሉ ለሙሉ ከታለመለት አላማ ውጪ ሲጠቀሙ የተገኙ 187 የህንፃ ባለቤቶች እያንዳንዳቸው 100 ሺሕ ብር እንዲቀጡ መደረጉን የአዲስ አበባ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ክበበው ሚደቅሳ ለአሐዱ እንደገለጹት፤ በቅርቡ ፀድቆ ወደ ሥራ በገባው የተሽከርካሪ ማቆሚያ አገልግሎት አሰጣጥ ደንብ መሰረት ጥፋተኛ ሆነው የተገኙት የሕንፃ ባለቤቶች የተጣለባቸውን የ100 ሺሕ ብር ቅጣት ከፍለዋል፡፡

ከእነዚህ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆኑትን የተሸከርካሪ ማቆሚያ ወይም ፓርኪንግ አገልግሎት ፈቃድ እንዲወስዱ መደረጉን ተናግረዋል።

ቦታውን ሙሉ ለሙሉ ወደ እቃ ማስቀመጫ እና ለንግድ አገልግሎት የማዋል ሥራ ሲሰራ እንደነበር ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ የተሽከርካሪ ማቆሚያውን በከፊል ለሌላ አላማ ያዋሉ አካላት ላይ ደግሞ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አስረድተዋል።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አክለውም፤ ሕንጻዎች ከዲዛይናቸው ጀምሮ የግንባታ ፈቃድ ሲሰጣቸው የራሱ የሆነ አላማ እንዳላቸው አብራርተዋል፡፡

ባለስልጣኑ በከተማዋ የትራፊክ አደጋን ለመከላከል፤ የተሽከርካሪዎችን እንቅስቃሴ ታሳቢ ባደረገ መልኩ የትራፊክ ፍሰቱ እንዲሳለጥ የሚያደርጉ የተለያዩ ሥራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡

በዚህም መሰረት ሕጉን ተግባራዊ በማያደርጉ አካላት ላይ አሁንም ቅጣቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለጹም ሲሆን፤ እስካሁን በስፋት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ እየተሰራ መቆየቱንም ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን የተሸከርካሪ ማቆሚያ ስፍራዎችን ማስተዳደር የሚያስችለውን፤ የተሽከርካሪ ማቆሚያ አገልግሎት አሰጣጥ ደንብ ቁጥር 165/2016 በከተማ አስተዳደሩ ጸድቆ በሥራ ላይ መዋሉ ይታወሳል፡፡

በዚህም ደንብ መሰረት ሕጉን በተላለፉ አካላት ላይ ከገንዘብ ቅጣት ጀምሮ የፍርድ ቤት ክስና የንግድ ፈቃድ ስረዛ ድረስ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ተመላክቷል፡፡

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 07:24


በጊዜያዊ አስተዳደሩ የተሾሙት ከንቲባ በጊዜያዊነት ወደ ቢሯቸው መግባታቸው ተገለጸ

ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የተሾሙት ከንቲባ አቶ ብርሃነ ገብረየሱስ በጊዜያዊነት ወደ ቢሯቸው መግባታቸውን በሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የክልሉ ቅርጫፍ ጽህፈት ቤት ለአሐዱ አስታውቋል፡፡

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት በዋነኝነት በሚቆጣጠረው የመቐለ ከተማ ምክር ቤት፤ ዶክተር ረዳኢ በርሃ የመቀሌ ከተማ ከንቲባ ሆነው እንዲሰሩ ባለፈው ጥቅምት ወር አጽድቆ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡

ይህንንም የተቃወመው የትግራይ ግዜያዊ አስተዳደር ደግሞ፤ አቶ ብርሃነ ገብረየሱስ የመቀሌ ከንቲባ ሆነው እንዲሰሩ ባለፈው ሕዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ሹመት ሰጥቶ ነበር።

ከዚህ ጋር በተያያዘ አሐዱ "ጉዳዩ ከምን ደረሰ?" ሲል የትግራይ ቅርጫፍ እምባ ጠባቂ ተቋምን ጠይቋል፡፡

ይህንንም ተከትሎ ግልፅ የአስተዳደር ክፍተት እየታየ መቆየቱን፤ የተቋሙ ኃላፊ አቶ ፀሀዬ እምባዬ ለአሐዱ በሰጡት ምላሽ ገልጸዋል፡፡

ቅርጫፍ ጽህፈት ቤቱ በዚህ አንድ ወራት ግዜ ውስጥ ሕዝቡ የት መሄድ እንዳለበት ጭምር ግራ ከመጋባት በተጨማሪ አገልግሎት ለማግኘት መቸገሩንም የገለጹት ኃላፊው፤ በአሁን ሰዓት ግን ችግሩ ተፈቶ በጊዜያዊ አስተዳደሩ የተሾሙት ከንቲባ አቶ ብርሃነ ገብረየሱስ ወደ ቢሯቸዉ መግባታቸውን ተናግረዋል።

በመቀሌ የነበረው ችግር በጊዜያዊነት እንደተፈታ የገለጹት አቶ ፀሀዬ፤ ይህ ችግር በአዲግራት እና በሌሎች የትግራይ ከተሞች ጭምር መኖሩንም ገልጸዋል፡፡

ቅርጫፍ ጽህፈት ቤቱ ሕዝቡ በብዙ መንገድ መቸገሩን ቢገልፅም፤ ፍርሃት በመኖሩ ቅሬታ ለማቅረብ የመጣ የከተማ ነዋሪ አለመኖሩን ተናግረዋል፡፡

ይህንን በመቃወም በሳለፍነው ሳምንት በመቀሌ ከተማ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ማህበረሰብ ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣት በጊዜያዊ አስተዳደሩ የተሾመ ከንቲባ ወደ ቢሮ እንዲገባ መጠየቁ የሚታወስ ነው፡፡

በህወሓት እና በጊዜያዊ አስተዳደር መካከል የተፈጠረዉን ውዝግብ ተከትሎ፤ የመቐለ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅሕፈት ቤት ከታሸገ አንድ ወር መቆየቱ ይታወሳል።

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Jan, 07:02


ከሰሞኑ በመጠኑ ከፍ ያለና በተደጋጋሚ ንዝረቱ በአዲስ አባባ ላይ የተሰማ የመሬት መንቀጥቀጥ ለሊቱን ተከሰተ

ታሕሳስ 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በትላንትናው ዕለት ለሊት 9 ሰዓት ከ52 ላይ እስከ ዛሬ ሲከሰት ከነበረው በመጠኑ ከፍ ያለና 5 ነጥብ 8 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአፋር ክልል አምቦሳ አካባቢ መከሰቱን የአሜሪካ የጂኦሎጂ ሰርቬይ መረጃ አመላክቷል።

የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ በተደጋጋሚ በስፋት ሲሰማ እንደነበርም አሐዱ በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች ከሚገኙ ነዋሪዎች ማረጋገጥ ችሏል። 

ይህም የመሬት መንቀጥቀጥ ሰሞኑን እየተከሰቱ ካሉ ርዕደ መሬቶች በመጠኑ ከፍተኛው ሲሆን፤ ረዘም ላሉ ሰከንዶች መቆየቱም ተነግሯል።

የመሬት መንቀጥቀጠለ የተከሰተው በአፋር ክልል ከአቦምሳ ከተማ 56 ኪሎ ሜትር ርቀት እንዲሁም ከአዳማ ከተማ 137 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ መሆኑን ተመላክቷል።

በተጨማሪም ትናንት ምሽት 2:01 ሰዓት ላይ በፈንታሌ ዙሪያ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 3 እንዲሁም፤ ቀን 11:27 ሰዓት ላይ በሬክተር ስኬል 5 ነጥብ 2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱም ተገልጿል፡፡

በሌላ በኩል በአፋር ክልል፣ ዱለሳ ወረዳ በተከሰት የመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ በበርካታ ሥፍራዎች ላይ ፍል ውሃዎች እየተፈጠሩ ይገኛሉ።

በመሬት መንቀጥቀጡ ሳቢያ በፈንታሌ እና በዶፈን ተራራ መካከል የተፈጠረው የመሬት ስንጥቅ ክፍተቱ እየጨመረ መሆኑንም የተገለጸ ሲሆን፤ በተራራው ላይ ጭስ እየወጣበት የነበረው ቦታ በአሁን ወቅት እሳት እየወጣበት እንደሚገኝ በአካባቢው ያሉ ምንጮች ጠቁመዋል።

የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል ከፍ ማለት ትርጉሙ ምንድነው? በሚለው ጉዳይ ላይ ከአሶሽየትድ ፕረስ እና ከሌሎች ምንጮች የተገኙ መረጃዎች ይህን ያመላክታሉ።

ቁጥሮቹ ሲተነተኑ (በሬክተር ስኬል):-

👉 ከ4 ነጥብ 0 በታች፤ አነስተኛ ነው፤ ትንሽ ብቻ ነው የሚሰማው። አልፎ አልፎ ጉዳት ያስከትላል።

👉 ከ4 ነጥብ 0 እስከ 4 ነጥብ 9 ድረስ፤ ጉዳቱ አብዛኛውን ጊዜ አነስተኛ ነው።

👉 ከ5 ነጥብ 0 እስከ 5 ነጥብ 9 ድረስ፤ መጠነኛ ነው። በደንብ ባልተገነቡ ሕንፃዎች ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።

👉 ከ6 ነጥብ 0 እስከ 6 ነጥብ 9 ድረስ፤ ጠንከር ይላል። ህዝብ በሚበዛባቸው አካባቢዎች በተለይም አሮጌ ወይም በደንብ ባልተገነቡ ህንፃዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል።

👉 ከ7 ነጥብ 0 እስከ 7 ነጥብ 9 ድረስ፤ መሠረተ ልማት እና ሕንፃዎች ሊያፈርስ ይችላል።

👉 እንዲሁም 8 ነጥብ 0 እና ከዚያ በላይ ሲሆን ደግሞ፤ ብዙ ጊዜ አስከፊ ጉዳት ማለትም የሰው ሕይወት መጥፋት እና ውድመት ሊያስከትል ይችላል። በተለይም በተከሰተበት አካባቢ ከባድ ጉዳት ያስከትላል።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተደጋጋሚ እየተከሰተ የሚገኘው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ በተለይም የክስተቱ መነሻ በሆኑ አካባቢዎች ላይ በሚገኙ ነዋሪዎች ላይ ስጋትን የደቀነ ሲሆን፤ በአካባቢዎቹ የሚገኙ ነዋሪዎችን ወደሌላ ስፍራዎች የማዘዋወር ሥራ እየተሰራ እንደሚገኝ እየተገለጸ ይገኛል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 15:42


የሕብረተሰቡ የግንዛቤ ዕጥረት በስራዬ ላይ ተግዳሮት ሆኖብኛል ሲል የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስታወቀ

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የዲጂታል መታወቂያ ምዝገባና፣ አሰጣጥ ሥራ ላይ የህብረተሰቡ የግንዛቤ ዕጥረት ችግር እንደሆነበት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ለአሐዱ አስታውቋል።

ብሔራዊ መታወቂያ የኢኮኖሚ ትስስርን በመፍጠር የዜጎችን የመተማመኛ ማዕቀፍ ለመዘርጋት የሚያስችልና የተቀላጠፈ አገልግሎት እንዲያገኙ የሚያስችላቸው ቢሆንም፤ የነዋሪዎች የግንዛቤ ዕጥረት ለውጥ ማምጣት አለመቻሉን በብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ውስጥ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ቃልኪዳን አብርሃም ተናግረዋል።

አክለውም ለሀገር ባለው እንድምታ እና ጠቀሜታ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እንዲሁም የምክክር መድረኮች ቢካሄዱም፤ በቂ ለውጥ ማምጣት አለመቻሉን ጠቁመዋል።

መታወቂያው ከደህንነት ጋር ተያይዞ ያሉ ችግሮችን ከመፍታት ባሻገር፤ ዲጂታል ኢትዮጵያን ለመገንባት ትልቅ ፋይዳ እንዳለውና ወንጀልን ለመከላከል የሚረዳ መሆኑን አክለዋል።

ከመታወቂያ ጋር ተያይዞ ያጋጥሙ የነበሩ ማጭበርበርን በመቅረፍ ረገድ አስተዋጽኦው የጎላ ስለመሆኑም አንስተዋል።

የብሔራዊ መታወቂያ ግንዛቤን በሕብረተሰብ ውስጥ በማስረፅ የተመዝጋቢዎችን ቁጥር ከመጨመር አንፃር እየተሰራ መሆኑን አሳስበው፤ ሕብረተሰቡም እገዛ እንዲያደርግ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዋ ጥሪ አቅርበዋል።

"ሕብረተሰቡ የተለያዩ ተቋማት አገልግሎት ለማግኘት በሚሄድበት ወቅት መታወቂያውን መያዝ አስገዳጅ መመሪያዎች በመፅደቃቸው፤ ከአላስፈላጊ መጉላላት እንዲድን የፋይዳ መታወቂያ ሊኖረዉ ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል።

ዲጂታል መታወቂያ ባለቤቶች ቁጥር ከ10 ሚሊዮን በላይ መሆኑን አንስተው ፤ቁጥራዊ መረጃዎች አጥጋቢ ቢሆኑም ከዚህ በላይ መሆን መቻል እንዳለበት ጠቁመዋል።

በአሁኑ ወቅት የፋይዳ መታወቂያ በሀገሪቱ ውስጥ ማንነትን በማረጋገጥ የሚሰጡ ማንኛውም አገልግሎቶች ላይ ማቅረብ ግዴታ እየሆነ የመጣ ሲሆን፤ የተለያዩ መንግሥታዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማትም አገልግሎት ለመስጠት የፋይዳ መታወቂያ የሚጠይቅ አስገዳጅ አሰራር በመጠቀም ላይ ይገኛሉ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም ባወጣው መመሪያ መሰረት ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ ሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት፤ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወይም የፋይዳ ቁጥር ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ የሚቀመጥ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ይህን ተከትሎም በርካታ ባንኮች በአዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ ቅርንጫፎቻቸው አዲስ ሒሳብ ለመክፈት ለሚመጡ ደንበኞች፤ የፋይዳ መታወቂያ ወይም የፋይዳ ልዩ ቁጥር መያዝ እንዳለባቸው በማሳሰብ ላይ ይገኛሉ፡፡

በወልደሐዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 15:23


ተፈናቃዮችን በአጀንዳ ማሰባሰቡ ላይ ማሳተፉን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ገለጸ

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በየክልሎች ባደረገው የአጀንዳ ማሰባሰብ ላይ ቁጥራቸውን በውል የማይታወቁ ተፈናቃዮችን ማሳተፉን ለአሐዱ ገልጿል።

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን እያካሄደ ባለው ምክክር አሳታፊ እና አካታች ለማድረግ ከሚሰራቸው ሥራዎች መካከል ተፈናቃዮችን ያማከለ ሥራ መሆኑን የተናገሩት የኮሚሽኑ ቃል አቀባይ አቶ ጥበቡ ታደሠ፤ በአብዛኛው በየክልሉ በተካሄዱ አጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቶች ላይ ተፈናቆዮችን ማካተታቸውን ተናግረዋል።

በመሆኑም ተፈናቃዮች ባሉባቸው ክልሎች አካባቢዎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት እንደሌላው የማህበረሰብ ክፍል ሁሉ እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን አቶ ጥበቡ ገልጸዋል።

ቁጥራቸውን በሚመለከት ከክልል ክልል የተለያየ ቁጥራዊ መረጃዎች እንደሚኖሩ የተናገሩት ቃል አቀባዩ፤ አንድ አንድ ክልሎች ላይ በተለይም ግጭት ባለባቸው ላይ በርከት የማለት ነገር መኖሩን ተናግረዋል።

በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ ቁጥሩ ሊያንስ እንደሚችል በማንሳት፤ በአጠቃላይ በአጀንዳ ማሰባሰብ የተሳተፉ ተፈናቆዮችን ቁጥር ማወቅ እንደማይቻል ገልጸዋል።

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ በአስር ክልሎችና በሁለት ከተማ አስተዳደሮች የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውን ያከናወነ ሲሆን፤ በቀጣይ በአማራ እና ትግራይ ክልል ለማካሄድ እቅድ እንዳለዉ ተናግሯል፡፡

"ለመሆኑ ምክክር ኮሚሽኑ በተለያዩ ክልሎች የሚገኙ ተፈናቃዮችን በክልል ደረጃ ሳይሆን እንደ አንድ ባለድርሻ በመቁጠር አጀንዳቸውን ለምን መሰብሰብ አልተቻለም?" ሲል አሐዱ ጠይቋል።

ቃል አቀባዩ በምላሻቸው፤ "ከአስር የማህበረሰብ ክፍሎች እንደ አንድ ተቆጠረው አጀንዳቸውን እያስረከቡ ነው" ሲሉ መልሰዋል።

በሌሎች ክልሎች እንደተደረገው ሁሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በተለይም 'በርካታ ተፈናቃይ ይገኝበታል' ተብሎ በሚታሰቡት በአማራ እና ትግራይ ክልልም አጀንዳ የማሰባሰቡ ላይ ተሳትፎ እንዲኖራቸው እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአሁን ሰዓት ከክልሎች በተጨማሪ በቀጣይ ከፌደራል ተቋማት የአጀንዳ ማሰባሰብ ሥራውን እንደሚሰራ ማስታወቁ አይዘነጋም።

ኮሚሽኑ በታሕሳስ ወር ሦስት ዓመቱን የሚደፍን ሲሆን የቆይታው ግዜ የሚጠናቀቅ በመሆኑ፤ የተወካዮች ምክር ቆይታውን እንደሚያራዝምለት ይጠበቃል።

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 14:52


በሀገር አቀፍ ደረጃ ፈቃድ ተሰጥቷቸው የሚሰሩት 34 የዘይት አምራቾች ብቻ መሆናቸዉ ተገለጸ

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ ሙሉ በሙሉ በሥራ ላይ ያሉ እውቅና የተሰጣቸው ዘይትን የሚያመርቱ ፋብሪካዎች 34 መሆናቸውን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገልጿል።

በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የገበያና ፋብሪካ ምርቶች ጥራት ማረጋገጥ ዲስክ መሪ ሥራ አስፈጻሚ ተከተል ጌቱ ከ34ቱ በተጨማሪ 4 ፋብሪካዎች ዘይት ወደ ማምረት ሂደት እየገቡ መሆኑን ለአሐዱ ገልጸዋል።

እነዚህ 34 ፋብሪካዎች በሀገር ዉስጥ ከሚያስፈልገው የዘይት ምርት 18 ነጥብ 3 በመቶውን እንደሚሸፍኑ አንስተዋል። አክለውም "አምራቾቹ የተቀመጠውን ደረጃ አሟልተው በሥራ ላይ የሚገኙ ናቸው" ብለዋል።

የዘይት ምርቶቹ ከኑግ፣ ከሱፍ አበባ፣ ከሰሊጥ እንዲሁም ከሌሎች የቅባት እህሎች እንደሚመረቱ ገልጸው፤ ምርቶቹ በከፊል የተጣሩ እንዲሁም ሙሉ በሙሉ የተጣሩ በሚል ተከፍለው እንደሚመረቱ ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል።

"ገበያ ላይ የሚገኙ ዘይቶች 'የጥራት ደረጃቸውን የጠበቁ ናቸው? ወይስ አይደሉም?' የሚለውን የገበያ ጥናት እናደርጋለን" ያሉም ሲሆን፤ ከደረጃ በታች የሆኑት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ተናግረዋል።

'ሕብረተሰቡ ላይ የጤና ጉዳት ያደርሳሉ' ተብለው የታሰቡ ምርቶች ናሙና ከገበያ ላይ እንደሚወሰድ የገለጹት መሪ ሥራ አስፈጻሚው፤ አምራቾቹ የት እንደሚገኙ የማይታወቁ ሲሆኑ ህብረተሰቡ ምርቶቹን እንዳይጠቀም በሚዲያ መረጃው እንደሚተላለፍ ጠቁመዋል።

ለዚህም በዘይት ምርቶቹ ላይ የሚቀመጠው አድራሽ እንዲሁም ስልክ ቁጥር የተሳሳተ የሚሆንበት አጋጣሚ መኖሩንም አንስተዋል።

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 14:18


በቡግና እና ላስታ ወረዳዎች የተከሰተው ድርቅና ግጭት ሳቢያ 77 ሺሕ ሰዎች መጎዳቸውን የአውሮፓ ኮሚሽን አስታወቀ

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ በቡግና እና ላስታ ወረዳዎች የተከሰተው ድርቅና ግጭት ሳቢያ 77 ሺሕ ሰዎች መጎዳቸውን እንዲሁም፤ 10 ሺሕ የሚሆኑ ደግሞ መፈናቀላቸውን የአውሮፓ ሲቪል ጥበቃ እና የሰብአዊ እርዳታ ኦፕሬሽንስ (ECHO) ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡

በቡግና እና ላስታ ወረዳዎች የተከሰተው ድርቅና ግጭት እየተባባሰ መምጣቱን የገለጸው ሪፖርቱ፤ በአካባቢው ባሉ ታጣቂ ሃይሎች የሚደረጉ ገደቦች ሕዝባዊ አግልግሎቶችን ለማግኘት ፈታኝ እንዳደረገው፣ የቴሌኮሙኒኬሽን እና የባንክ አገልግሎቶች ሥራ ላይ አለመሆናቸውን እንዲሁም የመንግሥት መዋቅሮች ለሦስት ወራት በስፍራው አለመኖራቸው አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም በአካባቢው ዝቅተኛ የሰብል ምርት፣ የምግብ ዋጋ መናር፣ የሰብዓዊና የማህበራዊ ጥበቃ ድጋፍ እጦት አሳሳቢ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ 79 በመቶ የሚሆኑ ነፍሰ ጡር እና የሚያጠቡ እናቶች እንዲሁም 70 በመቶ የሚሆኑ ጨቅላ ሕጻናት በየተመጣጠነ ምግብ እጥረት እየተጎዱ መሆኑን ገልጿል፡፡

ከዚህ ውስጥ "ዘጠኝ ነጥብ 2 በመቶ የሚሆኑት ሕጻናት እጅግ ከባድ የሆነ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት አለባቸው" ሲል አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም 5 ሺሕ 747 የወባ ሕመምተኞች እንደሚገኙና 77 በመቶ የሚሆነው ማህበረሰብ በውሃ እጦት እንደሚሰቃይ የገለጸው ሪፖርቱ፤ 35 በመቶ የሚሆኑ ሕጻናት ብቻ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት እየተከታተሉ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ገልጿል፡፡

የዓለም የምግብ ድርጅት እና የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር የምግብ እርዳታ ማድረግ መጀመራቸውን በማንሳት፤ በአውሮፓ ሲቪል ጥበቃ እና የሰብአዊ እርዳታ ኦፕሬሽኖች የገንዘብ ድጋፍ የምግብ፣ ውሃ እና የንጽህና መጠበቅያ ቁሳቁሶችን ለማቅረብ መቻሉንም በሪፖርቱ አስታውቋል፡፡

በዳግም ተገኝ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 13:22


#አሐዱ_ትንታኔ

"ከሞስኮ የተሰማው ተስፋ አስቆራጭ ዜና!"

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/jz7d8vJEHFU?si=GCA1UNN1nf7O6NTK

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 13:17


የቆዳ ምርትን ለማሳደግ ዘመናዊ ማሽንን በመጠቀም እርድ ማከናወን እንደሚገባ ተገለጸ

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የቆዳ እና ሌጦ ምርቶችን ለማሳደግ የሚረዱ የኬሚካል፣ የማሽን እና መሰል የኢንደስትሪ ምርቶች ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባ የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል አስታውቋል፡፡

ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ለቆዳ እና ሌጦ ምርቶች ግብዓትነት የሚውሉ ምርቶች በሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች የሚመረቱበትን የአሰራር ሂደትን ማሳደግ እንደሚገባም፤ በማዕከሉ የቆዳ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሚሻሞ ዋካሶ ተናግረዋል፡፡

አክለውም፤ ከውጭ ሀገር የሚገቡ ለቆዳ ምርት ግብዓትነት የሚውሉ ምርቶች በሀገር ውስጥ እንዲመረቱ የተሰሩ አንዳንድ ለውጦች መኖራቸውን አንስተዋል፡፡

"የቆዳ እና የሌጦ ውጤቶች በሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ በማቅረብ ገቢን ለማስገኘት ግን አሁንም መስራት ያስፈልጋል" ያሉ ሲሆን፤ ቆዳ ብቻውን የቆዳና ሌጦ ምርቶችን ገበያ ማሳደግም ሆነ ለውጥ ለማምጣት በቂ አለመሆኑን አንስተዋል፡፡

ሥራ አስፋጻሚው አክለውም፤ በባህላዊ መንገድ የሚከናወን የእርድ አገልግሎት የቆዳ ጥራት ላይ ተግዳሮት በመሆኑ ሊስተካከል እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በዚህም የቆዳ ምርትን ለማሳደግ ኢንዱስትሪዎች ላይ መሰራት እንዳለበት እና ዘመናዊ ማሽንን በመጠቀም እርድ ማከናወን እንደሚገባ ተናግረዋል።

በየቦታው የሚከናወን የእርድ አገልግሎት የቆዳ ጥራት ለማስጠበቅ አስቻይ አለመሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ከሌሎች ያደጉ ሀገራት ተሞክሮ በመውሰድ የእርድ አገልግሎቱ ዘመናዊ ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከሐምሌ ወር 2016 ጀምሮ እስከ ጥቅምት 2017 ዓ.ም ባሉት አራት ወራት ወደ ውጭ ከተላከ የቆዳና የቆዳ ውጤት ስምንት ነጥብ ሦስት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ማግኘቷን የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

ከዚህ ውስጥ ወደ አራት ነጥብ ዘጠኝ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የተገኘው የቆዳ ፋብሪካዎች ወደ ውጭ ከላኩት ምርት ሲሆን፤ ዜሮ ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ዶላሩ ደግሞ የቆዳ ጓንት አምራቾች ከላኩት ምርት የተገኘ ነው።

እንዲሁም ዜሮ ነጥብ ስድስት ሚሊዮን ዶላር የቦርሳ፣ አንድ ነጥብ አራት ሚሊዮን ዶላር ደግሞ ከቆዳ ተረፈ ምርት እሴት በመጨመር በመላክ የተገኘ መሆኑን ማዕከሉ ገልጿል።

ይህም የውጭ ምንዛሪ ገቢ ከሚጠበቀው በታች መሆኑን የጠቀሰው የቆዳና ቆዳ ውጤቶች ኢንዱስትሪ ምርምርና ልማት ማዕከል፤ በዘርፉ ያሉትን ተግዳሮቶች ለመፍታት እንዲሁም የቆዳ ምርቱን እና ጥራቱን ለማሳደግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቋል።

በእሌኒ ግዛቸው
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 12:14


በአዲስ አበባ ከዛሬ ጀምሮ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ይዞ መቅረብ አስገዳጅ መሆኑ ተገለጸ

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከዛሬ ታሕሳስ 23 ቀን 2017 ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ ባንኮች የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ይዞ መቅረብ ግዴታ መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።

ባንኩ ባወጣው መመሪያ መሠረት በዛሬው ዕለት በከተማዋ በሚገኙ ሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ወይም የፋይዳ ቁጥር ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ተደርጓል።

የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን የወሰዱ ዜጎች ቁጥር፤ 10 ሚሊየን መድረሱን ማስታወቁ ይታወሳል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 11:59


የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በሠራተኞቹ እና በአምቡላንሶቹ ላይ "ዘግናኝ" ጥቃት መፈጸሙን ገለጸ

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ ወረዳ እና በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ ለሕይወት አድን ተግባር በሚንቀሳቀሱ ሠራተኞቹ እና በአምቡላንሶቹ ላይ "ዘግናኝ" ጥቃት መፈጸሙን አስታውቋል።

ማኅበሩ "ባልታወቁ ኃይሎች በተተኮሰባቸው ጥይት የሁለቱም አምቡላንስ አሽከርካሪዎች ለከፍተኛ ጉዳት የተዳረጉ ሲሆን፤ አምቡላንስ ተሽከርካሪዎቹም ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡" ሲል ነው የገለጸው።

ማኅበሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሠራተኞቹን ጨምሮ በበጎፈቃደኞቹ እና ተሽከርካሪዎቹ ላይ በሚፈፀሙ ጥቃቶች አማካኝነት ሰብዓዊ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ወገኖች ለማድረስ ፈተና እየሆነበት እንደሚገኝ አስታውቋል፡፡

"በመሆኑም ጥቃት የሚፈፅሙ የትኛውም ተፋላሚ ኃይሎች ድርጊቱ ኢትዮጵያ የፈረመችውን ዓለም አቀፍ የጄኔቫ ሥምምነቶችን የሚፃረርና ከማኅበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ተረድተው፤ የማኅበሩ ሠራተኞች፣ በጎፈቃደኞችም ሆኑ ተሽከርካሪዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው ሰብዓዊ ተግባራቸውን ማከናወን እንዲችሉ፣ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ፣ ከመሰል ድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ማኅበረሰቡም ድርጊቶቹን እንዲያወግዝ የተለመደ ተማፅኗችንን እናቀርባለን፡፡" ብሏል።

የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር በተለያዩ አካባቢዎች በተጋጋሚ በታጣቂ ኃይሎች በሚፈጸም ጥቃት ምክንያት፤ በሠራተኞቹ ላይ የሕይወት ማለፍ እንዲሁም አምቡላንስ ተሽከርካሪዎቹ ላይ ቃጠሎ እና ውድመት እንደሚደርስበት ሲገልጽ መቆየቱ ይታወቃል።

ማኅበሩ በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫም፤ "የወገኖቻቸውን ሕይወት ለመታደግ ሲንቀሳቀሱ የጥቃት ሰለባ በመሆን መተኪያ የሌላት ውድ ሕይወታቸውን ላጡ ሠራተኞች እና በጎፈቃደኞች ቤተሰቦች መፅናናትን እንዲሁም ለተጎዱት በቶሎ ማገገምን" ተመኝቷል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Jan, 10:38


'የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚያደርገው ትግል' በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ፤ አሐዱ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ያዘጋጀው የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው

ታሕሳስ 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አሐዱ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን "አሐዱ መድረክ" በተሰኘው ሳምንታዊ ፕሮግራሙ በስቱዲዮ ከሚያደርገው ውይይት በተጨማሪ፤ ዛሬ ታሕሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም 'የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስጠበቅ የሚያደርገው ትግል' በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ የዲፕሎማሲ ባለሙያዎች፣ የፓለቲካ ባለሙያዎች፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ ፖለቲከኞች እንዲሁም የሀገር ጉዳይ የሚመለከታቸው አካላት የተሳተፉበት የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በውይይት መድረኩ "የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ ፖሊሲና ዲፕሎማሲ ብልህ የሆነ አገራዊ፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ ኑባሬዎችን ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው ወይ?፣ ዓለም አቀፉ የኃይል አሠላለፍ ምን ያህል ተፅዕኖ ሊኖረው ይችላል? እንዲሁም፤ የዲፕሎማሲ ታሪካችን ዳሰሳ የኢትዮጵያ ቀጣናዊ ዲፕሎማሲ የውስጥ አቅምን፣ ቀጣናዊና ዓለም አቀፋዊ የኃይል አሠላለፍና ሥርጭትን ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው ወይ?" የሚሉ መሠረታዊ የመወያያ ሀሳቦች ተነስተዋል።

በአሐዱ ሬዲዮ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ሊዲያ አበበ እና ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ መድረክ መሪነት እየተከናወነ በሚገኘው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የተገኙ እንግዶችም፤ የኢትዮጵያ የዲፕሎማሲ ግንኙነቶችን ከማጠንከር አንጻር 'ለሀገር ይጠቅማል' ያሏቸውን ሀሳቦች አንስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።

የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት ዶክተር ቆስጠንጢኖስ በርኸተስፋ "ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት በተለይም ከሱዳን፣ ከሶማሊያ እና ከኤርትራ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ማጠንከር ይገባታል" ያሉ ሲሆን፤ በዚህም በፖለታካዊ፣ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስሮች ላይ በደንብ መሰራት እንደሚገባት አሳስበዋል።

አክለውም "አሁን ላይ ኢትዮጵያ እንደሀገር ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ኢኮኖሚያዊ የጋራ ተጠቃሚነት ለማጠናከር፤ ዲፕሎማሲያዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ይበልጥ ትኩረት ማድረግ ይገባል" ብለዋል።

የቀድሞው የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር ፕሬዝዳንት እና ደራሲ ጌታቸው በለጠ በበኩላቸው፤ "ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለን የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት የግድ በፓለቲካ ብቻ መሆን የለበትም" ያሉ ሲሆን፤ "ስፖርት በራሱ ትልቅ ዲፕሎማሲን የሚያጠናክር መንገድ ነው" ብለዋል።

"ስለዚህም ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ለማስፋት፤ በአንድ አቅጣጫ ብቻ ሳይሆን የተለያዩ አማራጭ የዲፕሎማሲ አካሄዶችን መከተል እንደሚገባ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የአዲስ አበባ ኮሚቴ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አበበ አካሉ በበኩላቸው፤ "ዲፕሎማሲ የካድሬነት ሥራ አይደለም!" ያሉ ሲሆን፤ "ዲፕሎማሲ ጥበብ ነው፣ ሙያ ነው፣ እራሱን የቻለ ሳይንስ ነው እውቀት፣ ትምህርት እና መሰጠትን ይፈልጋል።" ሲሉ ተናግረዋል።

"የአንዲት ሀገር ንግድ፣ የሕዝቦች ስደት፣ የሀገር ደህንነት፣ ቴክኖሎጂ፣ ሥራ፣ እርዳታ፣ ትብብር፣ ድንበር፣ ሉዓላዊነት፣ ሰላም እና ግጭት በዲፕሎማቶች እና በምትከተለው የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ላይ ይመሰረታል።" ሲሉም አክለዋል።

በተጨማሪም "ጦርነት የዲፕሎማሲ ውድቀት ውጤት ነው! ዲፕሎማቶች ተደራዳሪዎች፣ ታጋሾች እና ተናግረው የማሳመን ብቃት ሊኖራቸው ይገባል።" ብለዋል።

"በፓለቲካው ላይ ያለው የዲፕሎማሲ ክፍተት የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነቶች ላይ ጉዳት አስከትሏል" ያሉም ሲሆን፤ "ከፖለቲካ አመለካከት ጋር የተቆራኘው ዲፕሎማሲያችን መላቀቅ አለበት" ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ ሰብሳቢ ዶ/ር ራሄል ባፌ በበኩላቸው፤ "ኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ እና ተቋም ቢኖራትም፤ የተሸረሸረ አካሒድ ውስጥ ተገብቷል" ብለዋል።

ይህንም ሲያብራሩ፤ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲው በፓርቲ እይታ ውስጥ በማስገባት፣ ለግል ፍላጎት በመሸነፍና በመንግሥታዊ እይታ ውስጥ ተከፋፍሎ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

"ነገር ግን እንደ ሀገር የሚጠቅመው መንግሥታዊና ተቋማዊ የሆነው ዲፕሎማሲ ላይ መሥራት በመሆኑ፤ እዚህ ላይ በደንብ ሊተኮር ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል።

"ከዲፕሎማቶች ሹመት ጋር በተያያዘም ከካድሬ ሹመት መውጣት ያስፈልጋል" ያሉ ሲሆን፤ ዲፕሎማሲውን እንዲመሩ የሚመረጡ ሰዎች የካድሬ ሥራ አስፈፃሚ እየሆኑ መምጣታቸው አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱን ገልጸዋል።

ለዚህ ደግም ከሁሉ በላይ የውስጥ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ሰላምን ማስፈንና በኢኮኖሚ ልቆ መገኘት እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

በተጨማሪም በመድረኩ የኢትዮጵያ የሕዝብ ለሕዝብ ዲፕሎማሲ፣ ፖለቲካዊ እንዲሁም ምጣኔ ሀብታዊ ግንኙነቶች ምን መምሰል አለባቸው? እንዲሁም፤ በሕዳሴ ግድብ እና በባህር በር ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ዙሪያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ምን አይነት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን መፍጠር ይገባል? በሚሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይቶች እየተደረጉ ይገኛል።

👉 ሙሉ ውይይቱን በነገው ዕለት በአሐዱ ሬድዮ 94.3 ላይ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት እስከ 5፡00 ሰዓት ድረስ በሚተላለፈው፤ "አሐዱ መድረክ" ፕሮግራም ላይ ይጠብቁን!

በተጨማሪም በአሐዱ ቴሌቪዥን እንዲሁም የዩቲዩብ ቻናል ላይ ሙሉ ውይይቱ ይለቀቃል። http://www.youtube.com/@AHADUTVNETWORK

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 17:05


#አሐዱ_ሳድስ

"ሊበጠስ የደረሰው የቻይና እና አሜሪካ ውጥረት" በአብይ ይልማ

ሙሉውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/lYDA5mhq9mQ?si=wiXUmcpqmOnpDhWf

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 15:45


ወደ መቶ ብር ከፍ ያለው የዩኒቨርሲቲዎች የቀን የምግብ በጀት የተለየ ለውጥ ያመጣል ተብሎ አይጠበቅም ተባለ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የዩኒቨርሲቲዎች በጀት 100 ብር ሆነ ማለት ድሮ ተማሪዎች ሲመገቡ ከነበረበት የምግብ አይነት የተለየ ለውጥ ይመጣል ማለት አይደለም ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

የዩኒቨርስቲዎች የምግብ በጀት በቀን ከ22 ብር ወደ 100 ብር መሻሻሉን ተከትሎ፤ ከሰሞኑ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚገኙ ተማሪዎች የምግብ ተመኑ ሲያድግ በተቃራኒው ግን የሚቀርበው የምግብ አይነትና መጠን ያነሰ በመሆኑ ቅሬታቸውን እያቀረቡ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ አሐዱም ይሄንን የተማሪዎች ቅሬታ በመያዝ ትምህርት ሚኒስቴርን አነጋግሯል።

በዚህም በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አስተዳደርና ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ዶ/ር ሰሎሞን አብርሃ በሰጡት ምላሽ፤ የምግብ በጀቱ 100 ብር ሆነ ማለት የግድ የተለየ ለውጥ ይመጣል ማለት እንዳልሆነ ገልፀው፣ "የምግብ አይነቱም ሙሉ ለሙሉ አስደናቂ በሆነ መልኩ ይቀየራል ማለት አይደለም፣ ሊቀየርም አይችልም" ሲሉ ገልጸዋል።

ድሮውንም ተማሪዎች በተመደበላቸው 22 ብር ብቻ ሲመገቡ እንዳልቆዩ የሚገልጹት ዶ/ር ሰሎሞን፤ "ከፌዴራል መንግሥት የሚመደበው 22 ብር አነስተኛ መሆኑ ስለሚታወቅ ዩኒቨርሲቲዎች በራሳቸው አካሄድ ሲያስተካክሉ ቆይተዋል" ብለዋል።

አሐዱም "የትምህርት ሚኒስቴር ያደረገው ማሻሻያ በቂ ነው ወይ? አሁን ካለው የገበያ ሁኔታ ጋርስ ተመጣጣኝ ነው?" ሲል ዩኒቨርስቲዎችን ጠይቋል።

የባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት መንገሻ አየነ የትምህርት ሚኒስቴር ለተማሪዎች የቀን ምግብ 22 ብር ቢመደብ፤ ከዛ በላይ ወጪ እንደበረው እና ተቋማቱ ለሌላ ሥራ የሚያገኙትን ገንዘብ ለምገባ የሚያውሉበት ሁናቴ መኖሩን ገልጸዋል።

"ዩንቨርስቲዎች በሚመደው 22 ብር ብቻ ተማሪዎቻቸውን አይመግቡም ነበር" ሲሉ ዶ/ር ሰሎሞን ያነሱትን ሃሳብ ተጋርተዋል።

"አሁን የተሻሻለው በጀት በተወሰነ ደረጃ ችግርን ይቀርፋል ተብሎ የሚጠብቅ ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ የተደረገው ማሻሻያ ቁጥሩ ትልቅ ቢመስልም ቀድሞ ሲወጣ ከነበረው ወጪ አንጻር ሲታይ አሁንም ተጽዕኖ እንደሚኖረው ገልጸዋል።

በአንጻሩ ሌላው አሐዱ ያነጋገራቸው የሰላሌ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ቶሎሶ ዳኒ፤ "አሁን ካለው የዋጋ ንረት አንጻር 22 ብር ተማሪዎችን መመገብ አይችልም ነበር፡፡ በተደረገው ጥናት መሰረት ወደ መቶ ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል" ያሉ ሲሆን፤ የተመደበው በተማሪ 100 ብር በቂ እንደሚሆንም ገልጸዋል።

በንጽጽር ሲታይ ቀድሞ ከነበረው 22 ብር ወደ መቶ ብር ከፍ መደረጉ ከፍተኛ የሆነ ጭማሪ መሆኑን አንስተዋል።

ዶ/ር ሰሎሞን የዩንቨርስቲዎቹን ፕሬዝዳንቶች ሃሳብ ሲያጠናክሩ፤ ዩኒቨርስቲዎች ከሚመደብላቸው የተለያየ በጀት እያዟዟሩ በቀን ከ80 እስከ 150 ብር በማውጣት ተማሪዎችን ሲመግቡ እንደነበር ገልጸዋል፡፡

የተማሪዎች የምግብ ሜኑ ከመሻሻሉ በፊት አንድ እንጀራን እስከ 24 ብር ድረስ የሚገዛ ዩኒቨርስቲ እንደነበረ ጠቅሰው፤ "ድሮ ይመደብ የነበረው በጀት አንድ እንጀራ እንኳን በቅጡ የማይገዛ ነበር" ሲሉ አክለዋል።

በመሆኑም ይህ አካሄድ የዩኒቨርሲቲዎችን እንቅስቃሴ ስላስተጓጎለና የአሰራር ስርዓታቸው ላይም ችግር ስለፈጠረ፣ የምግብ ሜኑ ሲዘጋጅ ጥናት ተጠንቶ ሀገር አቀፍ የተማሪ ህብረት ተወካዮች ጭምር በአካል በተገኙበት የዩኒቨርሲቲዎች ምግብ ማሻሻያ መደረጉን ለአሐዱ ተናግረዋል።

አክለውም ተማሪዎች አሁን ካለው ሁኔታ አንፃር ማድረግ ያለባቸው የሚመደብላቸው በጀት በአግባቡ ለእነርሱ መድረሱን እና በቀን የመቶ ብሩ በጀት ተሰልቶ በሳምንት 700 ብር ወጪ መደረጉን፣ እንዲሁም ያንን ወጪ ታሳቢ ያደረገ ሜኑ መቅረብና አለመቅረቡን ማረጋገጥ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ የተማሪዎች ህብረት አደረጃጀትም ሀላፊነት በመውሰድ በአግባቡ መከታተል እንዳለበት አፅንኦት ሰጥተዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 15:14


የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የወጣቱን የሥራ አጥነት ችግር ከመቅረፍ ይልቅ በፖለቲካ ሽኩቻው ላይ ትኩረቱን አድርጓል ሲል ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብት ኢትዮጵያ ወቀሰ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር የወጣቱን የሥራ አጥነት ችግር ከመቅረፍ ይልቅ በፖለቲካ ሽኩቻው ላይ ትኩረቱን አድርጓል ሲል "ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብት ኢትዮጵያ" የተሰኘው ሀገር በቀል የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅት ወቅሷል፡፡

ድርጅቱ "በክልሉ ያሉ ተቋማት መውደማቸው ለሥራ አጥነት ችግር መንስኤ ናቸው" ሲልም ገልጿል፡፡

በትግራይ ክልል በነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት ምክንያት ከሰው ሕይወት መጥፋትና ንብረት መውደም በተጨማሪ በወጣቱ ሕይወት ላይ ከፍተኛ ችግር መፍጠሩ ይገለጻል፡፡
በተለይም በቅርቡ የትግራይ ወጣቶች ማህበር እንዳስታወቀው ከሆነ፤ በክልሉ ሥራ ያላቸው ወጣቶች ከ20 በመቶ ያነሱ ናቸው፡፡

አሐዱም ይህንን የወጣቱን ችግርና በክልሉ ያለውን ሰብዓዊ ቀውስ በሚመለከት በክልሉ የቅድሚያ ሰብዓዊ መብቶች ለኢትዮጵያን ምክትል ፕሬዝዳንት መብሪህ ብርሃኔን ጠይቋል፡፡

ምክትል ፕሬዝዳንቱ በምላሻቸው በክልሉ አብዛኛውን ችግር የፈጠረው ጦርነት መሆኑን በማንሳት፤ "በተለይም በጦርነቱ ምክንያት ተቋማት መውደማቸው ለዚህ ምክንያት ነው" ብለዋል፡፡

እንደ ሀገር አቀፍ የሥራ ዕድል ችግሮች መኖራቸውን ያነሱት አቶ መብሪህ፤ ይሁን እንጂ በትግራይ ክልል ያለው ችግር ከሁሉም የከፋ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

"ይህንን ችግር ለመቅረፍም የግዚያዊ አስተዳደሩ በርካታ ሥራዎች መስራት ሲጠበቅበት በውስጥ ፖለቲካዊ ሽኩቻ ውስጥ ተጠምዷል" ሲሉ ወቅሰዋል፡፡

የትግራይ ክልል በድህረ ጦርነት ወቅት ላይ ያለ መሆኑን የሚያኑሱት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ "ወደ ቅድመ ጦርነት መመለስ ከባድ ሊሆን ቢችልም ቀስ በቀስ ለመመለስ ፖለቲካ ሽኩቻውን መቀነስ አለበት" ብለዋል፡፡

"ለዚህም በግዚያዊ አስተዳደሩና በህወሓት መካከል ያለው ሽኩቻ መቆም አለበት፤ ስልጣንም ከምርጫ ውጪ ሊገኝ አይችልም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

"በአሁኑ ወቅት በክልሉ ትልቅ ችግር ፈጥሮ የሚገኘው የፖለቲካው ውጥረት በመሆኑ ይህንን ችግር ለመቅረፍ የፌደራል መንግሥትም በመልሶ ግንባታ ላይ ሊሳተፍ ይገባል" ሲሉም ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 14:50


#አሐዱ_ስንክሳር

"መጪዋ ኢትዮጵያ ምን ትምሰል?" (በጥበቡ በለጠ)

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/KOwl9g30k40?si=wgrPwHrTaCd2Y6lZ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 14:42


ተአማኒነት ማጣትና የፖለቲካ አለመረጋጋት ግጭቶች በሀገር-በቀል ዕውቀቶች እንዳይፈቱ አድርጓል ተባለ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ በሁሉም አከባቢዎች በሚባል ደረጃ የሚፈጠሩ ግጭቶች በሰውና በሀገር ሐብት ላይ ከባድ አደጋዎች እንዳይስከስቱ ቅድመ መከላከል እና ግጭቶች ከተፈጠሩ በኋላ በሀገር በቀል ዕውቀቶች በሠላማዊ መንገድ ለመፍታት የፖለቲካው አለመረጋጋት ፈተና እንደሆነባቸው የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ምሁራን ለአሐዱ ተናግረዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነባር ማኅበረሰባዊ ዕውቀቶችን በምርምር በመደገፍ ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍ፣ አሁን እየተፈጠሩ የሚገኙ ችግሮችን ለመፍታትም ሀገር-በቀል እውቀቶችን ጥቅም ላይ እንዲያውሉ ይጠበቃል።

"ለመሆኑ ኢትዮጵያዊ ዩኒቨርሲቲዎች በየአካባቢው ያሉ ግጭቶችን በሀገር-በቀል የግጭት መፍቻ መንገዶች ለመፍታት ምን ጥረት እያደረጉ ነው?" ሲል አሐዱ ጠይቋል።

በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የአገው ጥናት ኢኒስቲትዩት ዳይሬክተር ብርሃኑ አሳዬ፤ ተቋማቱ በዋናነት ከሚሰሩት ማሕበረሰብ ተኮር ምርምር ሥራዎች ውስጥ አንዱ፤ ሀገር በቀል ዕውቀቶችን ለቀጣይ ትውልድ ማስተላለፍና በእነዚህ ሀገራዊ ሀብቶች አማካኝነት ግጭቶችን መፍታት እና ቅድመ መከላከል ሂደት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን በክልሉ የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ኃይሎች እና በመንግሥት መካከል ያለው አለመግባባት ወደ ውይይት እንዲመጣና በእርቅ እንዲደመደም የሚያደርጉት ጥረት፤ ከሁለቱም ወገን ተአማኒነት ማጣታቸው ማነቆ እንደሆነባቸው ገልጸዋል።

በሁለቱም የግጭቱ አካላት እጅ ሥር በሚገኙ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ለመስራት የፀጥታው ሁኔታ ችግር መፍጠሩንም የገለጹ ሲሆን፤ "በዋናነት ግና በሁለቱም ወገን ዕምነት ማጣት ትልቁ ማነቆ ነው" ብለዋል።

የችግሩን ጥልቀት ለማወቅ፣ ለመረዳት፣ ጥናት ለማድረግ ሁኔታዎች አስቻይ አለመሆናቸውን የገለጹት ዳይሬክተሩ፤ ችግሮችን በመቋቋም ምርምር ሥራዎች ተጠናክረው እየተሰሩ ስለመሆኑም ጠቁመዋል።

"በየጊዜው የሚፈጠሩ ችግሮችን ደረጃ በደረጃ እየተፈቱ የሚሄዱበት መንገድ እየተሰራ ነው" ሲሉም አብራርተዋል።

ሌላው አሐዱ ያነጋገራቸው አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ ተመራማሪ እና የባሕልና ቋንቋ ጥናት ተቋም ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሰዒድ አሕመድ፤ አካባቢው የሚስተዋሉ ግጭቶችን በሀገር በቀል ዕውቀቶች በመፍታት የሚታወቅ መሆኑን አንስተዋል።

ነገር ግን አሁን ካለው ነባራዊ ሁኔታ አንፃር በሌሎች አከባቢዎች የሚቀሰቀሱ ግጭቶችን ከመፍታት አንፃር ሥራዎች ቢሰሩም በቂ አለመሆኑን አክለዋል።

እንዲሁም "ከሌሎች ከፍተኛ ተቋማት ጋር በመቀናጀት መሰል ሁኔታዎችን አፈታት ዘዴዎች ላይ አጽንኦት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው" ሲል ገልጸዋል።

አሐዱ ያነጋገራቸው ምሁራኑ ከዚህን ቀደም ከሚያጋጥማቸው ፈተናዎች መካከል የበጀት እጥረት አንዱ እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፤ ይህንን ችግር ሲቀርፉ የሰላም እጦት በትልቁ እየፈተናቸው እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ግጭቶችን ለመፍታት ሀገረሰባዊ ዕውቀቶችን መጠቀም ዘላቂ ለውጥ ለማምጣት እንደሚያግዝ ምሁራኑ አጽንኦት ሰጥተውበታል።

በወልደሐዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 13:55


በአምስት ዓመት ውስጥ 1 ሺሕ 900 የሚሆኑ የቤት ሠራተኞች ላይ ጥቃት መፈጸሙ ተገለጸ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም ክልሎች በአምስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ብቻ 1 ሺሕ 900 የሚደርሱ የቤት ሠራተኞች ላይ ጥቃት መፈፀሙን የቤት ሠራተኞች መብት ላይ የሚሰራው አንድነት የኢትዮጵያ ቤት ሠራተኞች ህብረት አስታውቋል።

ይህ ቁጥራዊ መረጃ ከተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች፣ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዲሁም ሪፈር የተደረጉ እና ወደ ህብረቱ መጠለያ በመሄድ መረጃቸው የተያዙት ብቻ እንደሆኑ የገለጹት የህብረቱ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሂሩት አበራ፤ "በየቤቱ የተዳፈነና ያልተነገረ ስለሚኖር ቁጥሩ ከዚህ በላይ ሊሆን ይችላል" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል።

የቤት ውስጥ ጥቃት ሰለባ ከሆኑት ሠራተኞች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ፆታዊ ጥቃት የደረሰባቸው ሲሆን፤ በቂ የሆነ መረጃ ባለመኖሩ መፍትሄ ያላገኙ ሴቶች መኖራቸውንም ገልጸዋል።

ቀሪዎቹ ደግሞ የደመወዝ ንጥቂያ፣ ጉልበት ብዝበዛና ድብደባ ያጋጠማቸው እንደሆኑ አሳውቀዋል።

በአምስት ዓመቱ ውስጥ የተለያየ አካላዊና ስነልቦናዊ ጥቃት ለደረሰባቸው የቤት ሠራተኞች ከሚመለከተው አካል ጋር በመሆን ተገቢውን ድጋፍ መደረጉንም ተናግረዋል።

በዚህም ሠራተኞቹ ችግራቸውን በመፍታት ወደ ሥራ እንዲመለሱ እንዲሁም ወደ ቤተሰቦቻቸው እንዲቀላቀሉ መደረጉን የገለጹ ሲሆን፤ መሰረታዊ የሆኑ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ላይ ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን አንስተዋል።

"የቤት ሠራተኞች እንደ ዜጋ አልተቆጠሩም" የሚሉት የህብረቱ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ ሂሩት፤ ዝቅተኛ የደሞዝ መጠን ስላልተተመነላቸውና የሥራ ቅጥር ውል የሌላቸው በመሆኑ መረጃዎችን ለማሰባሰብና መብታቸውን ለማስከበር ፈታኝ እንደሆነ ለአሐዱ ገልጸዋል።

በተለይም ሕጻናት የቤት ሠራተኞችን በሚመለከት አሰሪዎቻቸው 'የሥጋ ዝምድና አለን እነሱ ሥራ ፈልገው ሳይሆን ልናሳድግና ልናስተምር ነው ያመጣናቸው' የሚል ምላሽን በሚሰጡበት ጊዜ፤ በሕግ አግባብ እነሱን ለመጠየቅ አዳጋች እንደሆነ ጠቅሰዋል።

ያም ሁኖ ግን ሕጻናቶች እየሰሩም ቢሆን መብላትና መኖር ስላለባቸው ቢያንስ ተገቢውን ክፍያ እንዲያገኙና የጉልበት ብዝበዛ እንዳይፈፀምባቸው አሰሪዎችንና ሠራተኞችን ያካተተ ስልጠና እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 12:59


በምስራቅ ወለጋ ዞን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በምስራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የሲቡ ሲሬ ወረዳ አስታውቋል፡፡

አደጋው የተከሰተው በተለምዶ ሲኖ ትራክ በሚል የሚታወቅ የጭነት ተሸከርካሪ እና የሕዝብ ማመላለሻ ሚኒ ባስ በመጋጨታቸው መሆኑ ተነግሯል፡፡

በአደጋው የ11 ሰዎች ሕይወት ከማለፉ በተጨማሪ 12 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም የንብረት ውድመት መድረሱን የወረዳው የትራፊክ ደህንነት ኃላፊ ኢንስፔክተር ፈዮ ቡሊ ገልጸዋል፡፡

በተለምዶ ሲኖ ትራክ በመባል የሚታወቀው የጭነት ተሸከርካሪ በተለያዩ አካባቢዎች ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ የሚገኝ ሲሆን፤ በዚህ ሰሞን ብቻ ከሞተር ሳይክል አሽከርካሪዎች እንዲሁም ከሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች ጋር በመጋጨት ተደጋጋሚ የትራፊክ አደጋዎች መከሰታቸውን አሐዱ ሲዘግብ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

ስለሆነም አሽከርካሪዎች በሰውም ሆነ በንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት ከሚያስከትለው የትራፊክ አደጋ እራሳቸውንም ሆነ ማህበረሰቡን ለመጠበቅ ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ሊያሽከረክሩ ይገባል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!

ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 12:45


በተቋማት የምልክት ቋንቋ የሚችል አስተርጓሚ አለመኖሩ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ክፍተት መፍጠሩ ተገለጸ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የምልክት ቋንቋ የሚችል አስተርጓሚ አለመኖሩ በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ላይ ክፍተት እየፈጠረ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

መስማት የተሳናቸው ዜጎች ጉዳታቸው አለመታየቱ ለተጨማሪ ጉዳት እየተዳረጉ እንደሚገኙና በተቋማት ላይ የምልክት ቋንቋ የሚችል አስተርጓሚ የማያገኙበት ሁኔታ ስለመኖሩ በኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ብሄራዊ ማህበር ፕሬዝዳንት ዩሀንስ ተክላይ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ መስማት ለተሳናቸው ዜጎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር እንዲሁም ለማብቃት፤ በጤና፣ በትምህርት እና በማንኛውም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የምልክት ቋንቋን የሚችል አስተርጓሚ እንዲኖሩ አስቻይ ሁኔታን መፍጠር እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

የኢትዮጵያ መስማት የተሳናቸው ማህበረሰብ ማብቃት ማህበር መስራች እና ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ትዕግስት አለማየሁ በበኩላቸው፤ ተቋማት መስማት ለተሳናቸው ዜጎች ምቹ አለመሆን፤ የምልክት ቋንቋን የሚችል አስተርጓሚ በተቋማት ላይ አለመኖር፣ በበቂ ሁኔታ የምልክት ቋንቋ ማሰልጠኛ እጥረት እንዲሁም በማበረሰቡ ዘንድ ለመስማት የተሳናቸው ዜጎች ያለው የተሳሳተ ግንዛቤ በዋናነት ለችግሮቹ ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

አክለውም ከመስማት መሳን በተጨማሪ ማንበብ እና መጸፍ የማይችሉ ተደራራቢ ጉዳት ያለባቸው ዜጎች ስለመኖቸው ገልጸዋል፡፡

በጤና ተቋማት እና በትምህርት ቤቶች፣ በትራንስፖርት እና በሥራ ቅጥር፣ በሥራ ፈጠራ እንዲሁም በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚሰጡ አግልግሎቶች መስማት የተሳናቸውን ያካተቱ ሊሆኑ እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

ማህበሩ በ2014 ዓም የተመሰረተ መሆኑን ገልጸው፤ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ማህበረሰቦችን ማብቃት ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ለአብነትም መስማት የተሳናቸው ሕጻናት ወላጆች የምልክት ቋንቋን መናገር አለመቻላቸው ከፍተኛ አሉታዊ አስተዋጾ በማሳደሩ በተለይም ማህበሩ መስማት በተሳናቸው ሕጻናት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

በመሆኑም ወላጆች ከልጆቻው ጋር መግባባት እንዲችሉ ለማስቻል ለሕጻናት እና ለወላጆች የምልክት ትምህርት ለማሰልጠን እየሰራበት እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡

በእሌኒ ግዛቸው
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!

ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 12:29


ውሳኔው የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን የማይተገብሩ ተቋማት ችግር እየፈጠሩበት መሆኑን ቁም ለአካባቢ ጥበቃ ማኅበር አስታወቀ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አካባቢን በመበከል ማኅበረሰቡ ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ተግባራትን የሚፈጽሙ ተቋማት ላይ የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ የሚሰራው "ቁም ለአካባቢ" የአካባቢ ጥበቃ ማኅበር፤ "የፍርድ ቤት ውሳኔዎችን የማይተገብሩ ተቋማት የቆምኩለትን የአካባቢ ጥበቃ ዓላማ እንዳላሳካ እንቅፋት ፈጥሮብኛል" ሲል ለአሐዱ ተናግሯል።

የማኅበሩ መስራችና የሕግ ባለሙያው መልካሙ ኦጎ እንደተናገሩት፤ ለትርፍ ያልተቋቋመውና በአካባቢ ጥበቃ ላይ የሚሰራው ማኅበር በመላው ኢትዮጵያ የአካባቢ ብክለት የሚያስከትሉ የግል እና የመንግሥት ተቋማት ላይ ክስ በመመስረት የአካባቢ ጥበቃ ሕጎች እና መመሪያዎችን እንዲያከብሩ ይሰራል።

ማኅበሩ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ባሉት 5 ዓመታትም በ6 ተቋማት ላይ ክስ መስርቶ የጥፋተኝነት ውሳኔ አሰጥቷል።

የፍርድ ቤት ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጭ የተፈፀሙ መሆናቸውን የገለጹት አቶ መልካሙ፤ የፍርድ ቤት ውሳኔ የተሰጠባቸውን ጉዳዮች የሚያስፈጽሙ አካላት የፍርድ ቤትን ውሳኔ ተቀብለው እየተገበሩ ባለመሆኑ ከተወሰነባቸው 6 ተቋማት መካከል ሦስቱ ውሳኔውን እንዳልተገበሩ ተናግረዋል።

አንዳንዶቹ ውሳኔዎች ከተላለፉ 2 ዓመት እና ከዚያ በላይ ቢያስቆጥሩም ተፈጻሚ አለመሆናቸው የማኅበሩ ስራ ላይ እንቅፋት ፈጥሯል ያሉ ሲሆን፤ ማኅበራቸው ውሳኔ ካሰጠባቸው ተቋማት በተጨማሪ ሌሎች 3 ተቋማት ላይ ክስ መስርቶ በክርክር ሂደት ላይ እንደሚገኝ ነግረውናል፡፡

የህግ ባለሙያው አቶ መልካሙ እንዳሉት የፍርድቤትን ውሳኔ አልተገበሩም የተባሉት ተቋማት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ንግድ ፅህፈት ቤት፣ የጉለሌ ክፍለ ከተማ ደንብ ማስከበር አገልግሎት እና በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የልማት እና ኮንስትራክሽን መምሪያ ናቸው።

በከተማ እንዲወጡ እና አሰራራቸውን እንዲቀይሩ የተወሰነባቸው ተቋማት ትዕዛዙን ባለመፈጸማቸው ማኅበረሰቡን ለአየር፣ ለድምፅ፣ ለውሃ ብክለት እንዲሁም ለመሬት መራቆት ዳርገውታል ብለዋል።

በእመቤት ሲሳይ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Dec, 11:22


በሰሜኑ ጦርነት የወደሙ ትምህርት ቤቶችን ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት የበጀት እጥረት ማጋጠሙ ተገለጸ

ታሕሳስ 18/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል ከሚገኙ የአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መካከል 96 በመቶ የሚሆኑት በጦርነቱ ምክንያት አገልግሎት መስጠት በማይችሉበት ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ለአሐዱ ገልጿል፡፡

የቢሮው የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተር ስዩም ሃጎስ፤ በጦርነቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን የትምህርት ተቋማት መልሶ ለመገንባትና የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ለማሟላት የበጀት እጥረት ፈታኝ እያደረገው መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም የአንድ ዓመቱን ትምህርት በ5 ወራት ውስጥ ብቻ እየሰጡ እንደሚገኙ አንስተው፤ አሰራሩን ለመቅረፍ እየሰራን ቢሆንም የመሰረተ ልማት አለመሟላት ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነባቸው ተናግረዋል።

በቅርቡ “ሀውዜን” አካባቢ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተገነባው የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤትም ከ1 ሺሕ 8 መቶ በላይ ተማሪዎችን አያስተናግድም ያሉት የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተሩ፡ እየተወሰደ የሚገኘው መፍትሔ ከተማሪዎቹ ቁጥር አንጻር ተመጣጣኝ እንዳልሆነ አንስተዋል።

ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በተጨማሪ ሌሎች 5 የውጭ ሀገራት የተራድኦ ድርጅቶች የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን መገንባታቸውንም ጨምረው ነግረውናል።

የ17 ወራት ደመወዝ ያልተከፈላቸው በክልሉ የሚገኙ መምህራን ጦርነቱ ካስከተለባቸው የስነ-ልቦና ችግር እንዲላቀቁ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባውም የኮምዩኒኬሽን ዳይሬክተሩ አሳስበዋል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በሕዳር ወር 2017 ባወጣው ሪፖርት በክል ከ1.24 ሚሊዮን በላይ ትምህርት ቤት መግባት የነበረባቸው ሕፃናት ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን መግለጹ ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም ተዘግተው ከቆዩ 2 ሺሕ 492 ትምህርት ቤቶች ውስጥ 2 ሺሕ 105 ያህሉን መልሶ መከፈታቸውን የገለጸ ሲሆን፤ የተቀሩት 387 ትምህርት ቤቶች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት መክፈት አለመቻሉን አስታውቋል፡፡

በዳግም ተገኝ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
ዋትስአፕ፦ whatsapp.com/channel/0029VajDfVZI1rcb05C5B22b
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 16:43


አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው የሀገሪቱ አካባቢዎች የኤሌትሪክ ኃይል መቆራረጥ ማጋጠሙ ተገለጸ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ዛሬ ምሽት ከ12 ሰዓት በኃላ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው የሀገሪቱ አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተቋርጧል።

አሐዱም በክልሎች ባደረገዉ ማጣራት ሀዋሳ፣ ጅማ ባህርዳር፣ ትግራይ፣ በጉራጌ ዞን እና ሌሎች አካባቢዎች ላይ በተመሳሳይ ሰዓት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ የሃይል አቅርቦቱ መቋረጡን ለማወቅ ችላሏ።

የኢትዮጵያ ኤሌትሪክ አገልግሎት ማምሻውን ባወጣው መረጃ፤ "ዛሬ ማምሻውን በሲስተም አለመረጋጋት በተፈጠረ ችግር የተነሳ በመላው ሀገሪቱ የኃይል መቋረጥ" ማጋጠሙን አስታውቋል።

የተቋረጠውን ኃይል ወደነበረበት ለመመለስ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በኩል ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም ገልጿል።

አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 16:19


የብሔር ብሔረሰቦች ቀንን ለማክበር ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸው ተገለጸ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ከተማ 19ኛው የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓልን ለማክበር ቅድመ ዝግጅት መደረጉን የዞኑ መንግሥት ኮምዩኒኬሽን ገልጿል።

የቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ገዛኸኝ ጩባ ለአሐዱ እንደተናገሩት፤ በዓሉ በይዘትም ሆነ በዝግጅት ደረጃ የተሻለ እንዲሆን በቅድመ ዝግጅት ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

አክለውም በዓላት ሲቃረቡ በተለያዩ ነገሮች ላይ የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ነጋዴዎችና አሽከርካሪዎች ላይ ቅድመ መከላከል እና መቆጣጠር ሥራዎች እንደተሰሩም ጠቁመዋል።

በተጨማሪም የሚከሰቱ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከት ጊዜያዊ ችሎት መጀመሩን አብራርተዋል።

በከተማው እየተከበረ የሚገኘውን ሀገራዊ ሁነት ተከትሎ የሚከሰቱ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከት በዋናው፣ በሼቻ እና በልማት ቀበሌ ባሉ ምድብ ችሎቶች እስከ በዓሉ ፍጻሜ የሚቆይ ጊዜያዊ ችሎት መጀመሩንም ለአሐዱ ተናግረዋል።

አያይዘውም በዓሉን ለማክበር የሚመጡ እንግዶችን ባህላዊ እሴቶቻችንን በጠበቀ መልኩ ነዋሪዎች መቀበል እንዳለባቸውና "በዓሉን የዞኑን ገፅታ በሚያጎላ መልኩ ለማክበርና በስኬት እንዲጠናቀቅ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና የዞኑ ሕዝብ የድርሻውን ሊወጣ ይገባል" ሲሉም ጥሪ አቅርበዋል።

19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን "ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ  አንድነት" በሚል መሪ ቃል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት፤ ነገ ሕዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ ይከበራል።

በወልደሀዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 12:45


#አሐዱ_መድረክ

"ከብልፅግና በላይ ብልፅግና እንሁን የሚሉ ፓርቲዎች አሉ" ከኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር መጋቢ ብሉይ አብርሃም ሐይማኖት ጋር የተደረገ ቆይታ (ክፍል 1)

ቆይታውን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
👇
https://youtu.be/A2MVQiNKxl4?si=hB0cfdjYzEs4feQZ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 12:30


በሩብ ዓመቱ በብልሹ አሰራር ተሳትፈዋል የተባሉ 46 ባለሙያዎች እና ተገልጋዮች ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በ2017 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት ከማዕከል እስከ ወረዳ ድረስ በብልሹ አሰራር ተሳትፈዋል ያላቸውን ባለሙያዎች እና ባለጉዳዮች ተጠያቂ ማድረጉን አስታውቋል።

ኤጀንሲው ከሚሰጣቸው የመታወቂያ የልደት ካርድ እና ሌሎችም የኩነት ምዝገባ አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ በተፈጸሙ የሌብነት፣ የሥነ-ምግባር ጉድለት እንዲሁም ከሃሰተኛ ሰነድ ጋር በተያያዘ 46 ባለሙያዎች እንዲሁም ግለሰቦችን ከቀላል እስከ ከባድ የሥነ-ምግባር እና የወንጀል ተጠያቂነት እርምጃዎች እንደተወሰደባቸው ነው የገለጸው፡፡

ከእነዚህም መካከል በቀላል ዲሲፕሊን 17፣ በከባድ 9 እና ጉዳያቸው በፍርድ ቤት የተያዘ 9 እንዲሁም፤ በማዕከሉ የማረጋገጥ አገልግሎት ለማግኘት የመጡ 11 ባለጉዳዮች በጥቅሉ 46 ባለሙያዎችና ባለጉዳዮች በሩብ ዓመቱ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተነስቷል።

የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከክፍለ ሀገር በመሸኛ የሚመጣን ነዋሪ በተመለከተ፤ "መረጃዎች ተጣርተው ወረፋ እየጠበቁ ካሉት ከ42 ሺሕ በላይ አገልግሎት ፈላጊዎች መካከል ትክክለኛ መረጃ ያላቸውን ከሕዳር አንድ ጀምሮ አስተናግዳለሁ" ያለ ቢሆንም እስካሁን አለመጀመሩም ይታወቃል።

አሐዱም "ይህን አገልግሎት ለምን ሕዳር አንድ ማስጀመር አልተቻለም?" ሲል የኤጀንሲውን የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ወይዘሮ ጀሚላ ረዲን ጠይቋል፡፡

"አገልግሎቱን ለማስጀመር የተገልጋዮችን ማስረጃ የማጣራቱ ሠራ እየተሰራ ነው። ተጣርተው የመጡ ማስረጃዎችም አሉ" ብለው፤ ነገር ግን በተባለበት ቀን ለማስጀመር የሲስተም ብልሽት እንዳጋጠመ እና አዳዲስ ተመዝጋቢዎችን አሻራ መውሰድ ባለመቻሉ እንደዘገየ ገልጸዋል፡፡

"ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር በተያያዘም እንደ ሀገር እየተሰራበት ያለ ነው። ከእኛ ጋርም በጋራ እየሰራን ቢሆንም፤ መታወቂያው ግን የእኛን የቀበሌ መታወቂያ አይተካም" ሲሉም የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሯ ተናግረዋል፡፡

በእመቤት ሲሳይ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 09:57


ኮሚሽኑ በትግራይ ክልል ሀገራዊ የምክክር ሥራ ለመጀመር ከክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፍቃድ ማግኘቱን አስታወቀ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል ለውይይትም ሆነ የተሳታፊ ልየታ ለማድረግ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን ሲያደረግ ቢቆይም፤ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ፍቃድ አለማግኘቱን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መግለጹን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

አሁን ላይ ከጊዜያዊ ከአስተዳደሩ ፍቃድ መገኘቱንና በቅርቡ ሥራ እንደሚጀር የተናገሩት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ናቸው፡፡

ክልሉ ምክክር ለማድረግ ፍላጎት እንዳለው የገለጹት ፕሮፌሰር መስፍን፤ ምክክሩ ከፕሪቶሪያው የሰላምም ስምምነት ጋር በተያያዘ ተፈፃሚ እንዲሆን ጥያቄዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከዚህ ቀደም በተደጋጋሚ ሲገለጽ እንደቆየው፤ ከታጣቂ ሃይሎች ጋር ውይይት ለማድረግ ፍላጎት እንዳለውና ሥራዎችን እየሰራ ቢሆንም ሳይሳካለት መቅረቱን ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

ዋና ኮሚሽነሩ አክለውም፤ በቤንሻንጉል ጉምዝ እና በጋምቤላ ክልል አጀንዳ የማሰባሰቡ ሥራ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ቢሆን ኮሚሽኑ ሂደቱን ማሳካቱን በመግለጽ፤ በምዕራብ ኦሮሚያም መሰል ሥራ የመስራት ፍላጎት እንዳለው ተናግረዋል፡፡

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአማራ ክልል አጀንዳ የማሰባሰብ ሥራውን የሚያግዙ አካላትን መረጣ ያካሄደ ሲሆን፤ በትግራይ ክልል ግን ምንም ዓይነት ሥራ አለመጀመሩ ይታወቃል፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ:www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡-https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 09:15


ለዜጎች በቂ ሆነ የሥራ ዕድል እስካልተፈጠረ ድረስ ሙስና እና ብልሹ አሰራር ስጋት መሆናቸው እንደማይቀር ተገለጸ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ 70 በመቶ የሚሆነው ወጣት ቢሆንም ሙስናን እና ብልሹ አሰራርን በጋራ ከመከላከል አንፃር በወጣቱ ላይ እየተሰራ ያለው ሥራ ዝቅተኛ መሆኑን የፌደራል ሥነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ይህንን ችግር ለመቅረፍ በስብዓናው መልካም የሆነ ወጣትን ማፍራት የአቅም ግንባት መሰጠት እንዳለበት፤ በኮሚሽኑ የአስቸኳይ ሙስናን መከላከል መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው ተናግረዋል፡፡

መሪ ሥራ አስፈጻሚው በዘንድሮው ዓመት በአለም ዓቀፍ ደረጃ ለ21ኛ ጊዜ የሚከበረውን የጸረ ሙስና ቀንን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ፤ ኢትዮጵያ ከ1999 ጀምሮ በተባበሩት መንግሥትታት ድርጅት የጸረ ሙስና ኮሚሽን የጸደቀውን ስምምነት ተቀብላ ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንደምትገኝ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም ይህ ስምምነት በርካታ ነጥቦችን የያዘ መሆኑን ገልጸው፤ አባል ሀገራትም በየ አምስት ዓመቱ ግምገማ ስለሚያቀርቡ ኢትዮጵያም ኃላፊነቷን እየተወጣች እንደምትገኝ አስረድተዋል፡፡

አክለውም "ለሙስናና ብልሹ አሰራር ተጋላጭነት ስጋት የሚሆኑ ችግሮችን ለመቀነስ ወጣቱን ባሳተፈ መልኩ በጋራ እና በተቀናጀ ስልት መግታት ካልተቻለ፤ ወጣቱ በመንግሥት አስተዳደር ላይ የሚያነሳው ቅሬታ ሊጨምር ይችላል" ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡ 

ይህን ታሳቢ በማድረግ በሀገር አቀፍ ደረጃ ስጋት ደቅኖ የሚገኘውን ሙስና እና ብልሹ አሰራር ለመቀነስ ወጣቱን በአቅም ግንባታ ማሳደግ  እንደሚያስፈልግ የፌደራል ሥነ ምግባርና ጸረ ሙስና  ኮሚሽን መከላከል ሥራ አስፈጻሚ አቶ ገዛኸኝ ጋሻው ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ሁኔታ ለዜጎች በቂ ሆነ የሥራ ዘርፍ እስካልፈጠረች ድረስ እንዲሁም በቂ የሆነ ገቢ እንዲኖራቸው  እስካልተመቻች ድረስ ሙስና እና ብልሹ አሰራርን ለመቀነስ ተግዳሮት እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡

በደረጄ መንግስቱ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 08:55


ቲክቶክ ለአሜሪካ ኩባንያ እንዲሸጥ ወይንም በሀገሪቱ አገልግሎት ከመስጠት እንዲታገድ የሚስገድድ ሕግ ወጣ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአሜሪካ የፌደራል ይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት በቻይና በተመሰረተው ባይትዳንስ ኩባንያ ሥር የሚገኘው የቲክ ቶክ መተግበሪያ፤ በሚቀጥለው ዓመት መጀመሪያ ላይ እንዲሸጥ ወይም እገዳ እንዲጣልበት የሚያስገድድ ውሳኔ አፅድቋል።

ውሳኔው ለአሜሪካ የፍትህ ሚኒስቴር እና ለመተግበሪያው ተቃዋሚዎች ትልቅ ድል እንደሆነና ለቲክቶክ ደግሞ፤ ከባድ ኪሳራን ሊያስከትል እንደሚችል ተመላክቷል፡፡

ውሳኔውን ተከትሎም የፍትህ ሚኒስቴሩ ኃላፊዎች "ውሳኔው ቻይና በአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነቶች ላይ የደቀነቻቸውን ስጋቶች ለመዋጋት ዴሞክራት እና ሪፐብሊካኖች ተመሳሳይ አቋም እንዳላቸው አመላካች ነው" ማለታቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

በአሜሪካ 170 ሚሊዮን የሚደርሱ ተጠቃሚዎች ያሉት ቲክ ቶክ፤ "የዜጎችን ግላዊ መረጃዎች ለቻይና መንግሥት አሳልፎ ይሰጣል" በሚል ለቀረበበት ክስ ያቀረበው ይግባኝ ውድቅ በመደረጉ ውሳኔው መተላለፉ ነው የተነገረው፡፡

ጠቅላይ አቃቤ ሕግ ሜሪክ ጋርላንድ ውሳኔው "የቻይና መንግሥት ቲክቶክን በመሳሪያነት እንዳይጠቀም ለማድረግ አስፈላጊ እርምጃ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ በበኩሉ፤ "አይን ያወጣ የንግድ ዘረፋ ነው" ሲል ውሳኔውን የተቃወመው ሲሆን፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን መተማመንና ግንኙነት እንዳይጎዳ አሜሪካ ጉዳዩን በጥንቃቄ መያዝ እንዳለባት አስጠንቅቋል።

የቲክ ቶክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሾው ዚ ቼው ለሮይተርስ በላኩት ኢሜል፤ "የዛሬው ዜና ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም የመናገር ነፃነትን ለመጠበቅ ትግሉን እንደምንቀጥል ለማረጋገጥ እንወዳለን" ማለታቸውን ዘገባው አመላክቷል፡፡

መተግበርያው ለአሜሪካ ኩባንያዎች ከመሸጥ ይልቅ መታገድ መምረጡን ተከትሎም፤ በሚቀጥሉት 6 ሳምንታት ውስጥ በአሜሪካ መስራት ሊያቆም እንደሚችል ተነግሯል፡፡

የባይት ዳንስ ኩባንያ ተመራጩ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዓለ ሲመታቸው ከመከናወኑ አንድ ቀን በፊት ውሳኔውን ካላሳወቀ የእግድ አደጋ እንደተጋረጠበት የተገለጸ ሲሆን፤ ኩባንያው በመጪዎቹ ቀናት ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ለማለት ማቀቀዱም ተነግሯል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 07:03


በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል 700 የሚጠጉ የማዕድን አልሚዎች መኖራቸው ተገለጸ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ወደ 700 የሚሆኑ የማዕድን አልሚዎች በሥራ ላይ እንደሚገኙ የክልሉ የማዕድን ሀብት ልማት ቢሮ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ደርበው ዘንቶ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ከእነዚህም ውስጥ በድንጋይ ከሰል ዘርፍ 450 ተቋማት ተሰማርተው በክልሉ በሥራ ላይ እንደሚገኙ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡

ቀሪዎቹ 250 ተቋማት ደግሞ በእምነበረድ ዘርፍ ፈቃድ ወስደው እየሰሩ መሆኑን የገለጹት ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተሩ፤ 10 ግራናይት አምራች ተቋማትም በክልሉ መኖራቸን ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም በማዕድን ልማት ዘርፍ ተሰማርተው ሥራ ለመጀመር በሂደት ላይ ያሉ ሌሎች ተቋማት መኖራቸውንም አክለው ገልጸዋል፡፡

ከዚህ ባሻገርም በክልሉ የማዕድን ሀብት የሚገኝበት ቦታ ድንበር አካባቢ እንደመሆኑ በተለይም የወርቅ ማዕድን በሔገወጥ መንገድ እንደሚወጣ የተገለጹት ዳይሬክተሩ፤ ፈቃድ የተሰጣቸው አካላት ብቻ እንዲሰማሩ በማድረግ የመከላከል ሥራ እየተሰራ ስለመሆኑ ተናግረዋል፡፡

በዚህም በክልሉ ከዚህ በፊት 6 ነጥብ 6 ኪሎ ግራም የሚገመት ወርቅ በሕገ-ወጥ መንገድ ሊወጣ ሲል መያዙ ነው የተገለጸው፡፡

በእመቤት ሲሳይ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 06:06


ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ የምታደርገው እንቅስቃሴ ለኢትዮጵያ ስጋት ሊሆን አይገባም ሲሉ ምሁራን ገለጹ

ሕዳር 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአለም ዓቀፍ ግንኙነት ላይ የመደራደር አቅምን ማሳደግ እንጂ፤ ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ የምታደርገው እንቅስቃሴ ለኢትዮጵያ ስጋት ሊሆን እንደማይገባ ምሁራን ገልጸዋል።

ቱርክ በኢትዮጵያ እና ሱማሊያ መሀከል የተፈጠረውን የባሕር በር ውዝግብ እንዲሁም ኢትዮጵያ ከሶማሌ ላንድ ጋር የተፈራረመችውን የመግባባቢያ ስምምነት ተፈጻሚነት እና ውጥረትን በተመለከተ መፍትሄ የማፈላለግ ጥረቷን እንደምትገፋበት ማስታወቋ አይዘነጋም።

ይሁን እንጂ ቱርክ ከቀጠናው አባል ሀገራት ጋር የተለያዩ ወታደራዊ ግንኙነቶችን ስታደርግ ይስተዋላል። "በተለይም ለሶማሊያ የጦር መሳሪያ የማቅረብ እንዲሁም ወታደርን እስከ ማሰልጠን መድረሷ የኢትዮጵያ ደህንነት እና የወደብ ጥያቄ ላይ ተጽዕኖ አይፈጥርም ወይ?" ሲል አሐዱ የአለም ዓቀፍ ግንኙነት ምሁራንን ጠይቋል።

ከዚህ ጋር ተያይዞ ቱርክ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መሀከል ያለዉን የባህር በር ዉዝግብ ለማደራደር ብትሞክርም፤ ከሁለቱም ሀገራት ጋር የቆየ ወታደራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶች ያላት መሆኑን የገለጹት የቀድሞ ዲፕሎማት ዳያሞ ዳሌ ናቸው።

አክለውም ቱርክ እንደ ማንኛዉም ሀገር ጥቅሟን ከማስከበር አንጻር እንደምትመለከተው ሁሉ፤ እንዲሁ ኢትዮጵያም የዲፕሎማሲ ጥቅሟን እና ግንኙነቷን ማጠናከር እና የቀጠናውን እንቅስቃሴ በትኩረት ልታየው እንደሚገባ ገልጸዋል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምን ለማስከበር የምትከተለውን የውጭ ፓሊሲ እንደየአካሄዳቸዉ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚገባት የቀድሞ ዲፕሎማት ዳያሞ ዳሌ አሳስበዋል።

የቀድሞ አምባሳደር ጥሩነህ ዜናዉ በበኩላቸው፤ "ኢትዮጵያ የወደብ ጥያቄዋን ለማስመለስ ከቀጠናው ሀገራት እንዲሁም ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን መልካም ግንኙት ከማጠናከር እና የተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ፓለቲካዊ እና ቀጠናዊ ትስስርን ከመፍጠር አንጻር  'እንዴት የመደራደር አቅምን ማሳደግ እንዲሁም ቀጠናዊ ትስስርን እንዴት መፍጠር እችላለሁ' የሚለዉ እንጂ ቱርክ በቀጠናው እያደረገች ያለዉ እንቅስቃሴ ሊያሳሳስበን አይገባም" ብለዋል።

ምሁራኑ አክለውም ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ እና በቀጠናው የምታደርገው እንቅስቃሴ እና የማደራደር ሚናዎች ከኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ ጥቅም አንጻር ቢታዩም ኢትዮጵያም የጦር መሳሪያዎችን ስታቀርብ የነበረች ሀገር ከመሆኗ አንጻር እንዲሁም ከሁሉም ሀገራት ጋር የቆየ ታሪካዋ ወዳጅነት አላት ያሉ ሲሆን፤ "ከሶማሊያ ጋር ወታደራዊ ግንኙነት መፍጠሯ የሚጠበቅ ነው። ነገር ግን በጥንቃቄ ነገሮችን ማጤን ያስፈልጋል" ብለዋል።

በፅዮን ይልማ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 06:05


#ADVERTISMENT
#ጊፍትሪልስቴት
ታላቅ የምስራች
!
**
ጊፍት ሪል ስቴት ከ10% ቅድመ ክፍያ ጀምሮ በ22 ሳይቶቹ ቅንጡ አፓርትመንቶችን እና የንግድ ሱቆችን ለሽያጭ አቅርቧል፡፡

ይህ ሳይት ለአፓርትመንትና ንግድ ሱቆች የሚውሉ G+25 ሶስት መንታ ህንጻዎች ያሉት ሲሆን የዚህ 6ኛ መንደር መለያዎች፡-
•ከባለአንድ እስከ ባለአራት መኝታ ክፍሎች ያሉት፣
•ለመኖሪያም ሆነ ለንግድ ተመራጭ አካባቢ የሆነ፣
•በአንድ ወለል ሶስት ቤቶች ብቻ ያሉት፣
•በእያንዳንዱ ወለል ስድስት አሳንስር ያለው፣
•አራት ቤዝመንት ያሉት በቂ የመኪና ማቆሚያ የተዘጋጀለት፣
•24 ሰዓት የኤሌክትሪክ፣ ኢንተርኔትና ውሃ አቅርቦት አሉት፣

ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!
ለበለጠ መረጃ፡-
Website: https://www.giftbusinessgroup.com                                                                                             
Twitter: https://twitter.com/GIFTBusinessG                                                     
YouTube: www.youtube.com/channel/UCcqr7cpVv9ski-F7haxXx4w                                                     
Facebook: www.facebook.com/profile.php?id=100090918391017...                                                       
Telegram: https://t.me/giftbusinessgroup

Short Code: 8055

AHADU RADIO FM 94.3

07 Dec, 06:00


መልካም ቀን!
አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

AHADU RADIO FM 94.3

06 Dec, 15:31


በመንግሥትና በኦነግ ሸኔ ከፍተኛ አመራር መካከል የተደረገው ድርድር የስምምነት ነጥቦች ይፋ ሊደረጉ እንደሚገባ ፓርቲዎች ገለጹ

ሕዳር 27/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር የነበሩት ጃል ሰኚ ነጋሳ በአዲስ አበባ ከተማ የሰላም ስምምነት መፈራረማቸው መገለጹ ይታወቃል።

ጃል ሰኚ ነጋሳ መንግሥት ያቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ በመቀበል ነው ከአቶ ሽመልስ አብዲሳ ጋር የሰላም ስምምነቱን መፈረማቸው የተጠቆመው።

"ስምምነት መደረጉ ለረጅም ጊዜ የሰላም ጥያቄውን ሲያቀርብ ለኖረ ማህበረሰብ እፎይታን የሚሰጥ እና የሚበረታታ ነው" ያሉት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ (ኢፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ ናቸው።

ነገር ግን የዚህ ቡድን አመራር አስቀድሞ ወደ ጫካ የገባው 'ያልተመለሱ ጥያቄዎች ስላሉኝ ነው' ማለቱን አስታውሰው፤ "አሁን ምላሽ አግኝቶ ነው" ወይ ሲሉ ይጠይቃሉ።

አክለውም፤ "የተደረገው ስምምነት በምን በምን ጉዳዮች ላይ የጋራ መግባባት ተደርሶ መሆኑን፣ ከዚህ በኋላ መተዳደሪያ የሚሆኑ ነገሮች ተመቻችተዋል፣ ታጥቀው የነበሩ አካላትስ በምን ሁኔታ ነው የሚታዩት የሚለውን ግልጽ መድረግ ነበረበት" ሲሉ ለአሐዱ ገልጸዋል።

"ስምምነቱን የፈረመው አመራር ቡድን አስቀድሞ እጁን ሰጥቶ የነበረ ነው" ያሉት ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ፤ ከዚህ ቀደም እጃቸውን የሰጡ አመራሮችም እንዲሁም ተዋጊዎች እንደነበሩ አንስተዋል።

በመንግሥትና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት አመራር መካከል የተደረገውን ድርድር "የሰላም መጥፎ የጦርነት ጥሩ የለውም" በማለት የቀደመውን ሃሳብ የሚጋሩት የነጻነት እና እኩልነት ፓርቲ አደረጃጀት እና አመራር ዘርፍ ኃላፊው ሙባረክ ረሺድ በበኩላቸው፤ "ድርድሩ መደረጉ በጎ ነው" ብለዋ።

ይኼው ስምምነት በመርህ እና በተግባር ውጤት የሚታይበት ሊሆን እንደሚገባም ገልጸዋል።

"በመንግሥት በሽብረትኝነት የተፈረጀው የአሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከስምምነቱ ይፋ መደረግ በኃላ ባወጣው መግለጫ 'ከቡድኑ የተሰናበተና እኛን የማይወክል ነው' ማለቱ የራሱን ጥላ አጥልቷል" ያሉም ሲሆን፤ መንግሥት ዘላቂ ሰላም ማምጣት የሚችልበትን መንገድ መከተል እንዳለበት አሳስበዋል።

እንዲሁም "ኅብረተሰቡ ከስምምነቱ የሚጠብቃቸው በርካታ ነገሮች አሉ" በማለት፤ "ስምምነቱ ምን ምን ነገሮችን ይዟል ከምን ምን ይጠበቃል የሚለው ይፋ መደረግ አለበት" ሲሉ ገልጸዋል።

"ኅብረተሰቡም በተለያዩ ክልሎች ሰላም በማጣት ሰርቶ በመብላት ችግር ውስጥ ነው" ያሉት ፖለቲከኞቹ፤ መንግሥት ዘላቂ ሰላም ለማስፈን የሚያስችሉ ስምምነቶችን በተገቢው መንገድ መከተል አለበት ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል።

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር እና በጃል ሰኚ ነጋሳ መካከል የተፈረመውን ስምምነት አስመልክቶ፤ የስምምነት ሰነዱ ምን ይዟል፣ ምን ምን ጉዳዮች ላይ መግባባት ተደርሷል እንዲሁም የሰላም ስምምነቱ ተፈጻሚነት እስከምን ድረስ ነው የሚለው ጉዳይ በይፋ አለመገለጹ በብዙዎች ዘንድ ጥያቄ እየፈጠረ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል፡፡

ስምምነቱን ተከትሎም የኦሮሚያ ክልል መንግሥት ይህ የሰላም ስምምነት ለዜጎች እረፍትን የሚሰጥ ሰላም የሚያሰርጽ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፤ "ክልሉን ወደ መደበኛ ሁኔታ ለማምጣት እንዲህ ያሉ እምርጃዎች ይበረታታሉ" ብለዋል።

የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር የነበሩት ጃል ሰኚ ነጋሳ በዛሬው ዕለት በሰጡት መግለጫ፤ የሰላም ጥሪውን የተቀበሉት የሕዝብና የመንግሥትን ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎች ተከትሎ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ እየደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስ እና የሰላም አማራጭን መቀበል 'ብልህነትና አዋቂነት' መሆኑን በመረዳታቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

06 Dec, 14:32


በመዲናዋ 2 ሺሕ 400 ያለ አግባብ የዋጋ ጭማሪ አድርገው የሸጡ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱ ተገለጸ

ሕዳር 27/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በተያዘው የ2017 ዓ.ም ሩብ ዓመት የዋጋ ዝርዝር ሳይለጥፉና ምርትን በፍጥነት ወደ ገበያ ባለማስገባታቸው ምክንያት፤ 2 ሺሕ 400 በሚሆኑ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡

በቢሮው የገበያ መረጃ ጥናትና ማስተዋወቅ ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ሙሰማ ጀማል ለአሐዱ እንደገለጹት፤ ቢሮው በነጋዴዎች ላይ ቁጥጥር በማድረግ አስተዳደራዊና ሱቆችን የማሸግ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል፡፡

በዚህም መሰረት በሩብ ዐመቱ እርምጃ ከተወሰደባቸው መካከል 634 ሱቆች መታሸጋቸውን የገለጹ ሲሆን፤ እንዲሁም የዋጋ ዝርዝር ያለጥፉ 1 ሺሕ 800 በሚሆኑ ነጋዴዎች ላይ ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች መውሰዳቸውን ተናግረዋል፡፡

የታሸጉ ሱቆች ወደ ሥራ ገበታቸው እንዲመለሱ ከማድረግ አንጻር አስተዳደራዊና የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ በመውሰድ እንዲሁም ስህተታቸውን በማመን የመግባባት ሥራ ተፈጥሮ ወደ ሥራ እንዲመለሱ የተደረገበት ሁኔታ መኖሩንም አቶ ሙሰማ አክለው ገልጸዋል፡፡

የእርምጃ አወሳሰድ ሁኔታ በተመለከተ ነጋዴዎች የጹሑፍ ማስጠንቀቂያ፣ አስተዳደራዊ እርምጃ፣ ሱቆችን ማሸግ እንዲሁም በሕግ የተቀጡ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ሕገ ወጥ ንግድን እና ከተቀመጠው መመሪያ ውጭ የሚያካሄዱ ነጋዴዎችን ለመቆጣጣር ከሚመለከተው አካል በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙ ጠቁመው፤ ማህበረሰቡም በተለጠፈው የዋጋ ተመን ልክ ብቻ እንዲገዛ ቁጥጥር እያደረጉ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Nov, 16:34


#አሐዱ_ስንክሳር

የፅላተ-ሙሴ መቀመጫ አክሱም ፅዮን (በጥበቡ በለጠ)

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/gDsImnNlkx8?si=YwyXOibMO68dilSD

AHADU RADIO FM 94.3

30 Nov, 14:07


በኢትዮጵያ በየዓመቱ መከላከል በሚቻሉ በሽታዎች ምክንያት 95 ሺሕ ሕጻናት እንደሚሞቱ ተነገረ

ሕዳር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ የሳምባ ምችን ጨምሮ መዳን በሚችሉና ቀላል በሆኑ በሽታዎች ሳቢያ፤ በየዓመቱ ከአምስት ዓመት በታች የሆኑ 95 ሺሕ ሕጻናት እንደሚሞቱ ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

በተለይም መከላከል የሚቻሉ ሆነው ሕጻናት ከሚሞቱባቸው ዋና ዋና ምክያቶች መካከል፤ በቀዳሚነት የሚቀመጠው የሳምባ ምች መሆኑን በጤና ሚኒስቴር የጨቅላ ሕጻናትና ሕጻናት ዴስክ ኃላፊ መለስ ሰለሞን ለአሐዱ ተናግረዋል።

መዳን የሚችሉ በሽታዎች ሆነው ነገር ግን የሕጻናት ሕይወት እየነጠቁ ከሚገኙ በሽታዎች መካከል የሳምባ ምች 17 በመቶውን የሞት ምጣኔ እንደሚይዝ ገልጸዋል። "ነገር ግን የሳምባ ምችን ክትባት ከማስከተብ ጀምሮ ክትትል ከተደረግ መከላከል የሚቻል ሆኖ እያለ፤ ለሕጻናት ሞት ምክንያት ሆኗል" ብለዋል።

ከሳምባ ምች በመቀጠል በሁለተኛው ደረጃ መዳን የሚችል ሆኖ ሳለ ለሕጻናት ሞት መንስኤ በመሆን የተቀመጠው ተቅማጥ ሲሆን፤ በሌላ በኩልም ከተወለዱ እስከ 28 ቀን ላሉ ጨቅላ ህፃናት ዋና ዋና ገዳይ ከሚባሉት መካከል ቀናቸው ሳይደርስ መወለድ፣ ኢንፌክሽን እና መታፈን መሆናቸውን ኃላፊው አክለዋል።

ለዚህም በምክንያትነት ከሚጠቀሱት መካከል የግንዛቤ እጥረት፣ በቅርቡ ጤና ጣቢያ ማግኘት አለመቻል፣ የመንገድ ችግር፣ መድኃኒትን ጨምሮ ባለሙያ የሚፈልገውን ያህል አለማግኘት ተጠቃሽ መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከኢትዮጵያ ሕዝብ ከ83 በመቶ በላይ የሚሆነው ነዋሪነቱ ገጠር ከመሆኑ አንፃር፤ ከጤና ተቋም ተደራሽነት አኳያ የራሱ የሆነ ተፅዕኖ አለው ያሉት ኃላፊው፤ ይሁን እንጂ በትክክል መታከም ከቻሉ መዳን የሚችሉ በሽታዎች በመሆናቸው የጤና አቅርቦት፣ ስልጠና እና የማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራዎችን በመስራት እንዲቀንስ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ምንም እንኳን ሕጻናት የሚለው ትርጓሜ እንደ ዓለም ጤና ድርጅት ከተወለደ እስከ 18 ዓመት መሆኑን ያስታወሱት አቶ መለስ፤ "እንደ ኢትዮጵያ ትኩረት ተሰጥቶ የሚሰራው ግን ከአምስት ዓመት በታች ባሉ ሕጻናት ላይ ነው" ብለዋል።

ለዚህም ምክንያቱ "ከሕዝብ ብዛት አንፃር ተደራሽነት ከግምት ውስጥ መግባት ዋነኛው ይሁን እንጂ፤ ሕጻናት አምስት ዓመት ከተሻገሩ በሌሎች ነገሮች ካልሆነ በስተቀር የሳንባ ምችን ጨምሮ መዳን በሚችሉ በሽታዎች የተነሳ ለሞት የሚዳረጉበት ሁኔታ አስጊ ባለመሆኑ ነው" ሲሉ አስረድተዋል።

የጨቅላ ሕጻናትና ሕጻናት ፕሮግራም በተለየ መልኩ ትኩረት ተሰጥቶ ከሚሰራባቸው ፕሮግራሞች መካከል አንዱ እንደሆነም ተመላክቷል። ነገር ግን አሁን ድረስ መዳን በሚቻሉና ቀላል በሆኑ በሽታዎች የተነሳ በርካታ ሕጻናት ለህልፈት እንደሚዳረጉ ይገለጻል።

በአበረ ስሜነህ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Nov, 13:34


"ብልፅግና ከሀሳብ እንጂ ከሰዎች ጋር ግጭት ውስጥ አይገባም" ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

ሕዳር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምስረታ በዓል የማጠቃለያ መርኃ ግብር፤ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝደንት ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ተካሄዷል።

በዓደዋ መታሰቢያ በተካሄደው መርኃ ግብር ላይም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ፤ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ተመስገን ጥሩነህ፣ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የክልል ርዕሰ መስተዳደሮች እና የከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዲሁም የፓርቲውና የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።

በመርኃ ግብሩ ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ፓርቲው ወደ ስልጣን ከመጣበት ጊዜ አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ ያከናወናቸውን የዲፕሎማሲ፣ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ እንቅስቃሴ ያብራሩ ሲሆን፤ በዚህም "በፖለቲካው ዘርፍ የብልጽግና ፓርቲ አዲስ የፖለቲካ ልምምድ በኢትዮጵያ አስጀምሯል" ብለዋል።

ከዚህ ቀደም ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር መስራት እንዳልነበር ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በጠላትነት የመተያየት ባህልን ማስቀረት መቻሉን ገልጸዋል።

"ብልፅግና ከሀሳብ እንጂ ከሰዎች ጋር ግጭት ውስጥ አይገባም" ያሉም ሲሆን፤ "የሀሳብ ልዕልና የብልጽግና ፓርቲ ባህሉ ነው" ሲሉም መናገራቸውን ከፓርቲው ማኅበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

በተጨማሪም የብልፅግና ፓርቲ ከ 15 ሚሊዮን በላይ አባላት ያሉት የአፍሪካ ግዙፉ ፓርቲ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ በኢኮኖሚው ዘርፍም ባለፉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ የበጋ ስንዴ ማምረት የጀመረችበት፣ ሥራ አቁመው የነበሩ ኢንዱስትሪዎች ወደ ሥራ የገቡበት፣ ሜጋ ፕሮጀክቶች የተመረቁበት እንደነበር አንስተዋል።

በዲፕሎማሲ በኩልም ባለፉት 5 ዓመታት ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር እየሰራች ያለችው በወዳጅነት እና በትብብር መሆኑን ጠቁመዋል።

በመርሐ ግብሩ መልዕክት ያስተላለፉት የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ በበኩላቸው፤ "የበዓሉ ዓላማ ፓርቲው ከምሥረታው ጀምሮ እስካሁን ያደረገውን ጉዞ ለመዘከር እና ቃላችንን ለማደስ ነው" ብለዋል።

ፓርቲው በርካታ ፈተናዎች ቢያጋጥሙትም ፈተናዎችን ወደ ድል በመቀየር ድል ማስመዝገቡን ጨምረው ተናግረዋል፡፡

የብልጽግና ፓርቲ 5ኛ ዓመት የምስረታ በዓል "የሀሳብ ልእልና ለሁለንተናዊ ብልጽግና" በሚል መሪ ሀሳብ በተለያዩ ሁነቶች ሲከበር መቆየቱ ይታወሳል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Nov, 10:38


ሙስና እና ብልሹ አሰራር በኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የአሰራር ስርዓት ላይ ስጋት መደቀኑ ተገለጸ

ሕዳር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የአሰራር ስርዓት ላይ ሙስና እና ብልሹ አሰራር እየተስፋፋ ነው ሲል የፌዴራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

በተደጋጋሚ በሙስና እና ብልሹ አሰራር ክስ ሲቀርብበት የሚታየው የኢምሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ለዜጎች የሚሰጠውን አሰራር እያዘመነ መሆኑን ቢያሳውቅም፤ አሁንም ድረስ ቅሬታ እየቀረበበት ይገኛል፡፡

በቅርቡ እንኳን ከፓስፖርት ቅጣት የተሰበሰበ ወደ 18 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ በግለሰብ አካዉንት ገቢ ሲደረግ እንደነበር በኦዲት መረጋገጡና በምክር ቤት መቅረቡ የሚታወስ ነው፡፡

ይህን ሕገ-ወጥ አሰራራ ሲሰራ የቆየው ደግሞ ተቋሙ ባላወቀው መመሪያ እና ሕግ እንደሆነ የፊደራል ዋና ኦዲተር ገልጿል፡፡

አሐዱም "በተደጋጋሚ በተቋሙ ላይ የሚታዩ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለምን መቅረፍ አልተቻለም? እናተስ እንደተቋም ምን እየሰራችሁ ነው?" ሲል የፌዴራል የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽንን ጠይቋል፡፡

የኮሚሽኑ የሥራ አመራር ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ተስፋዬ ሸሜቦ በሰጡት ምላሽ፤ "ተቋሙ ለዜጎች በሚሰጣቸው የአሰራር ሂደቶች ላይ ስጋት እንዳለ መመልከት ችለናል" ብለዋል፡፡

ኮሚሽኑ በቀጣይ በይበልጥ መሰራት አለባቸው በሚባሉ ጉዳዮች ላይ እንደተቋም እንደዚህ አይነት ለዜጎች አስጊ የሆኑ አሰራሮችን ለመከታተል የሚያስችል ቴክኖሎጂ እያስተዋወቀ መሆኑንም ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"በኢትዮጵያ በሚገኙ በሁሉም ተቋማት ላይ ሙስና እና ብልሹ አሰራር አለ" ያሉት አቶ ተስፋዬ፤ "ነገር ግን ይህንን ለመቀርፍ የሥነ ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን መከላከያ ሚኒስቴርን ጨምሮ በሌሎች ተቋማት የሚገኙ አመራሮችን ስልጠና እየሰጠን ነው" ብለዋል፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር የ2015 እና 2016 በጀት ዓመት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና ውጤታማነትን በተመለከተ የክዋኔ የኦዲት ሪፖርት ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውይይት ባደረገበት ወቅት፤ የኤምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ስልጣን ሳይሰጠዉ ከፓስፖርት የሚገኝ የቅጣት ገንዘብ ሲሰበስብ መቆየቱ መገለጹ ይታወሳል፡፡

በዚህም አገልግሎቱ የገንዘብ ሚኒስትርን ሳያስፈቅድ የራሱን አካዉንት በመክፈት 17 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር ገደማ ገቢ ስለማድረጉ ተነግሯል።

አሐዱ ለተጨማሪ መረጃ የኢምግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ተደጋጋሚ ስልክ ሙከራ ያደረገ ቢሆንም ማግኘት አልቻለም። ነገር ግን ተቋሙ ምላሽ ለመስጠት ፍቃደኛ ከሆነ ምላሹን ወደእናንተ የምቀርብ ይሆናል።

በደረጄ መንግስቱ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Nov, 09:46


በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት ከሦስት እስከ አራት ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገለጸ

ሕዳር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአፋር ክልል በተከታታይ በተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦች ምክንያት ከሦስት እስከ አራት ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገልጿል፡፡

በክልሉ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ከስድስት መቶ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት መማሪያ ክፍል ውጭ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ፤ የአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሙሳ ሀሰን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው ባለፉት ጊዜያት በተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጦች ምክንያት፤ ከሦስት እስከ አራት ሚሊየን ብር የሚገመት ንብረት ላይ ውድመት መድረሱን አስረድተዋል፡፡

ከክልል ትምህርት ቢሮ እና አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት የትምህርት ስርዓቱን ከመማሪያ ውጪ ለሚከታተሉ በመቶች ለሚቆጠሩ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ድጋፍ እየተሰባሰበ እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡

የትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊው አክለውም፤ በክልሉ ከዚህ በፊት ከአራት ነጥብ ስምንት በላይ ሬክተር ስኬል መጠን ሲከሰት የነበረው የመሬት መንቀጥቀጥ፤ በአሁኑ ወቅት እየተስተዋለ እንዳልሆነ ተናግረዋል፡፡

ነገር ግን በወረዳው የሚስተዋለው የመሬት መንቀጥቀጥ በድንገት የሚከሰት መሆኑን ተከትሎ፤ ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ እና ተማሪዎቹ ትምህርታቸውን በድንኳን እና ከመማሪያ ክፍል ውጭ እየተከታተሉ ስለመሆኑ ተነግሯል፡፡

አክለውም በመሬት መንቀጥቀጥ ምክንያት በመማሪያ ሕጻዎች ላይ የደረሱ ውድመቶች ለመጠገን ተጨማሪ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡

በእሌኒ ግዛቸው
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Nov, 08:51


በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የቤት ውስጥ ጾታዊ ጥቃት እየተባባሰ መምጣቱ ተገለጸ

ሕዳር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በቤት ውስጥ የሚፈጸም ጾታን መሠረት ያደረገ ጥቃቶት እየጨመረ መምጣቱን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ አስታውቋል።

በክልሉ በሕጻናትና አፍላ ወጣቶች ላይ በቅርብ ሰዎች አማካኝነት አስገድዶ መድፈር፣ ግድያ እና ጾታን መሠረት ያደረገ ጥቃት መፈጸም እየተስፋፋ መምጣቱን ለአሐዱ የገለጹት፤ የክልሉ ሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኩሪባቸው ታንቶ ናቸው።

አሐዱም "የችግሩ መስፋፋት ከታወቅ ለምንስ መቆጣጠር እና መከላከል አልተቻለም?" ሲል ኃላፊዋን ጠይቋል።

በምላሻቸው ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች መበራከት፣ የሕግ ክፍተትና መላላት እንዲሁም የግንዛቤ ማነስ ጥቃቱ እንዲስፋፋ ምክንያት መሆኑን የገለጹ ሲሆን፤ በርካታ ሥራዎች ቢሰሩም የሚፈለገውን ያክል ለውጥ ማምጣት አለመቻሉን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ባለትዳር ሴቶች ለቤት ውሰጥ ፆታዊ ጥቃት ተጋለጭነታቸው የሰፋ መሆኑንም ጠቁመዋል።

ኃላፊዋ አክለውም ከፌዴራል አካላት ጋር በመሆን ችግሩን ለመቅረፍ እየተሰራ እንደሚገኝ ለአሐዱ ገልጸዋል።

ለቤት ውሰጥ ጾታዊ ጥቃት ተጋላጭ ለሆኑ ሰዎች የተለያዩ ኢኮኖሚያዊና ሥነልቦናዊ ድጋፎች እየተደረጉ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የችግሩን ግዝፈትና የሚያስከትለውን ጉዳት በመረዳትም ማሕበረሰቡ መሰል ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን ከመፈጸም መቆጠብ እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

በወልደሀዋርያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Nov, 07:02


የዝቅተኛ የደሞዝ ወለል ውሳኔ መዘግየቱ አሳስቦኛል ሲል ኢሰማኮ አስታወቀ

ሕዳር 21/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) መንግሥት የዝቅተኛ የደሞዝ ወለል ለመወሰን የየያዘውን ዕቅድ ሊያዘገየው ይችላል መባሉ አሳስቦኛል ሲል የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን አስታውቋል።

መንግሥት የዝቅተኛ ደሞዝ ወለልን ለመወሰን ጥናት አጥንቶ የጨረሰ ቢሆንም፤ "ችግር ያመጣብኛል በሚል ስጋት አዝግይቼዋለው" ማለቱን ተገቢ አይደለም ሲሉ የኮንፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ካሳሁን ፎሎ ለአሐዱ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንቱ "ይህንን በሚመለከት ለሚመለከተው የፌደራል የስራና ክህሎት ሚኒስቴር ምላሽ እንዲሰጠን ስንል ጠይቀናል" ብለዋል።

"በተጠና ጥናት መሠረት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ያመዝናል" የሚል ነገር መነገሩን የገለጹት አቶ ካሳሁን፤ "ጥናት በትክክል ተደርጎ ከሆነ በጥናቱ ላይ መሳተፍ ነበረብን" ብለዋል።

አቶ ካሳሁን አክለውም "እንደተባለው ኮሚሽኑን ሳያካትቱ ተጠንቶም ከሆነ ጥናቱን እንዲሰጡን ስንል በደብዳቤ ጠይቀናል" ሲሉም ተናግረዋል።

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ ሠራተኞች ማህበራት ኮንፌዴሬሽን ከኑሮ ውድነት ጋር ተያይዞ የስራ ግብር እንዲቀነስ እና የዝቅተኛ ደመወዝ ወለል የሚወስን የደመወዝ ቦርድ እንዲቋቋም ሲጠየቅ ይሰማል።

በኢትዮጵያ የሚገኘው የኑሮ ሁኔታ በቋሚ ደምወዝ በሚኖሩ ተቀጣሪ ሠራተኞች ላይ እየፈጠረ ያለው ተጽእኖ ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ እንደሆነ ይገለጻል፡፡

"የኑሮ ውድነቱ ሠራተኛው ከሚያገኝው ገቢ ጋር ሊመጣጠን ባለመቻሉ ዜጎች በአስቸጋሪ ሁኔታ ላይ ኑሯቸውን እንዲገፉ አስገድዷል" ያለው የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን፤ ማስተካካያዎች እንዲደረጉ በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲያቀርብ መቆየቱን አስታውቋል፡፡

ዝቅተኛ የደመወዝ ወለል እንዲወሰን እና የግብር ቅነሳ እንዲደረግ ኢሰማኮ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በነበረው ውይይት ጥያቄ ማቅረቡ የሚታወስ ሲሆን፤ ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን በደብዳቤ ቢጠይቅም ተገቢውን ምላሽ አለማግኘቱ ይገለጻል፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 18:31


#አሐዱ_ወንዞች

ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/xhpwUL9w2zI?si=7kgJ-Todxf4DjOWB

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 18:02


መንግሥት የሠራተኞችን የመጠቀም ዕድል እስካላመቻቸ ድረስ የሚሰሩበትን የሥራ ሰዓት ቢጨምር ውጤታማ አይሆንም ተባለ

ሕዳር 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የፌደራሉ መንግሥት የሠራተኞችን የመጠቀም ዕድል ቅድሚያ ሰጥቶ እስካላሻሻለ ድረስ፤ የሰዓት ጭማሪ ብቻውን በሕግ ቢያጸድቅ፤ ውጤታማ ሊያደርደገው አይችልም ሲሉ አሐዱ ያነጋገራቸው የሕግ ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡

አሐዱ ከሰሞኑ የመንግሥት ሠራተኞች ከዚህ ቀደም በሳምንት ሲሰሩ የነበረውን የ39 ሰዓት ወደ 48 ሰዓት ከፍ አድርገዉ እንዲሰሩ የሚያስገድደዉን ረቂቅ አዋጅ መሰረት በማድረግ፤ “በሠራተኞቹ ላይም ሆነ በመንግሥት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አያሳድርም ወይ? እንዲሁም ከአለም ዓቀፍ ሕግጋት አንጻር እንዴት ይታያል” ሲል ጠይቋል፡፡

የሕግ ባለሙያው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ በሰጡት ምላሽ፤ "አንድ ሰው በአለም ዓቀፍ ሕግ በቀን መስራት ያለበት 8 ሰዓት ነው" ብለዋል፡፡

ከዚህ በላይ ከሆነ ግን እንደ ድርጅቱ እና ሠራተኛው ፍቃደኝነት የሚወሰን መሆን እንዳለበት አስረድተዋል።

የውሳኔውን ረቂቅ አዋጅ በሁለት መልኩ እንደሚመለከቱት የገለጹት የሕግ ባለሙያው፤ በአንድ በኩል መንግሥት በሠራተኞች ላይ የሰዓት ጭማሪ ሲያደርግ የደሞዝ ጭማሪም ማድረግ እንዳለበት ጠቁመው፤ "በሌላ መልኩ ደግሞ በመንግሥት ላይ የሚያሳድረው አሉታዊ ተጽዕኖ ቀላል የሚባል አይደልም" ሲሉ ተናግረዋል።

ሌላኛው የሕግ ባለሙያ አቶ ወንድሙ ኢብሳ በበኩላቸው፤ "በምንም አይነት መልኩ በሠራተኛ ላይ አንድ ተቋም ሥራ ሲጨምር ሆነ የሥራ ሰዓት ሲያራዝም በዛው ልክ የሠራተኛውን ደሞዝ ማሻሻል አለበት" ባይ ናቸው፡፡

"ነገር ግን ይህን ማድረግ ካልተቻለ አመርቂ ውጤት ማምጣት አይቻልም" ብለዋል፡፡

"ሠራተኞችን ሳያስፈቅዱ አስገድዶ ለማስራት መሞከር ሀገርን ለይበልጥ ኪሳራ ማጋለጥ እንጂ ግብ የሚያመጣ ለውጥ ማምጣት አይቻልም" ሲሉም የሕግ ባለሙያዎቹ ተናግረዋል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሳምንቱ መጀመሪያ ሕዳር 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባከናወነው 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች አዋጅን ለማሻሻል የቀረበለትን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ ማጽደቁ ይታወሳል።

በደረጄ መንግስቱ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 17:25


#UPDATE
በአለልቱ ወረዳ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

👉 በ40 ሰዎች ላይ ከባድና 11 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሷል


ሕዳር 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አለልቱ ወረዳ በደረሰው የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት አስታውቋል።

ዛሬ ጠዋት 2:30 ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ የሚጓዝ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ሲኖ ትራክ ተሸከርካሪ ጋር በመጋጨቱ አደጋው መከሰቱን በስፍራው ካሉ ነዋሪዎች ሰምቶ አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል።

በአደጋው በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውንና የሲኖ ትራክ ተሸከርካሪው ረዳት መኪና ውስጥ ተቀርቅሮ በመቅረቱ እርሱን ለማውጣት ከአንድ ሰዓት በላይ ጥረት ቢደረግም ሕይወቱን ማትረፍ አለመቻሉን ነዋሪዎቹ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በአደጋው እስካሁን የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፋን እንዲሁም፤ በ40 ሰዎች ላይ ከባድ እና 11 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን የዞኑ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሥራ ሒደት ሃላፊ አቶ ሰለሞን ዘውዴ ለኤፍቢሲ ተናግረዋል።

በአደጋ የተጎዱ ሰዎች በሰንዳፋ ሆስፒታል ሕክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተመላክቷል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 15:05


ጾታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን ከመከላከል አኳያ የሕግ ክፍተት መኖሩ ተገለጸ

ሕዳር 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ጾታን መሠረት ባደረጉ ጥቃቶች ላይ እየተደረገ ያለ ቅደመ መከላከል ሥራ ቢኖርም እንደ ሀገር የሕግ ክፍተት መኖሩን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒሰቴር ለአሐዱ አስታውቋል።

ከችግሩ ጋር ተያይዞ የጥቃቱ ፈፃሚ አካላት በሕግ ቁጥጥር ሥር ከዋሉ በኋላ የሚበይነው ውሳኔ አስተማሪ አለመሆኑ ተነስቷል፡፡

በተለይም የተቀመጠው ሕግ በሥራ ቦታ ላይ የሚደርሱ ጥቃቶችን ብቻ እርምጃ የሚወሰድባቸው በመሆኑ፤ በሥራ ባልደረባ አማካኝነት ከሥራ ገበታ ውጭ  የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለመከላከል የሕግ ክፍተቶች መኖራቸውን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስቴር ዴኤታ ሂክማ ከይረዲን ተናግረዋል፡፡

የሕግ ክፍተቶች በመኖራቸው ሳቢያ በስፋት እየተስተዋለ የመጣዉን የአስገድዶ መድፈር፣ ግድያ እና ፆታን መሠረት ያደረገ ጥቃትን ለመቆጣጠር እና ለመከላከል አስቻይ አለማድረጉን ሚኒስቴር ዴኤታዋ ገልጸዋል፡፡

አክለውም ቀድመዉ የወጡ ነገር ግን በጊዜያቸው ትክክል የነበሩ ውሳኔዎች፤ አሁን ላይ 'አስተማሪ አይደሉም' ተብሎ የተለዩ ሕጎች ተለይተው እንዲሻሻሉ ጥናት ተደርጎ መጠናቀቁን ጠቁመዋል።

በቀጣይ በየደረጃቸው ካሉ በሚመለከታቸው ተወካዮች ምክር ቤት አና ከፍትሕ አካላት ጋር በቅንጅት በመወያየት የተለዩ ሕጎች ማሻሻያ እንዲደረግ እና ድርጊቱን ፈፃሚዎችን አስተማሪ እንዲሆን ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በወልደሐዋሪያት ዘነበ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 13:41


"የማሳልፋቸውን ውሳኔዎች እና እቅዴን ለመገናኛ ብዙሃንም ሆነ ለንግዱ ማህበረሰብ የማሳወቅ ግዴታ የለብኝም" ብሔራዊ ባንክ

ሕዳር 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተለያዩ ጊዜያት የማሳልፋቸውን ውሳኔዎች እና እቅዴን ለመገናኛ ብዙሃንም ሆነ ለንግዱ ማህበረሰብ የማሳወቅ ግዴታ የለብኝም ሲል ገልጿል።

ባንኩ ይህንን ያለው ከንግዱ ማሕበረሰብና የምጣኔ ሐብት ባለሙያዎች ተደጋግሞ ለሚነሳበት ጥያቄ መልስ ሲሰጥ ነው።

ብሔራዊ ባንክ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማሻሻያን በተመለከተ ያሳለፋቸው ገንዘብ ነክ ፖሊሲዎች ከማዕከላዊው መንግሥት አስተዳደር የታቀዱ መሆናቸውን ለአሐዱ የተናገሩት፤ በባንኩ የውጭ ምንዛሪ ቁጥጥር ምክትል ዳይሬክተር አቶ አበባየሁ ዱራፌ ናቸው።

ምክትል ዳይሬክተሩ ባንኩ ያደረጋቸው ማሻሻያዎች ኢኮኖሚው እንዲሻሻልና የአገር ገቢ እንዲያድግ ጉልህ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

ማዕከላዊ ባንኩ እስካሁን የገንዘብ ስርዓቱን ለዘብተኛ በሆነ መንገድ እየመራው እንዳለም ጠቅሰው፤ አጠቃላይ ፖሊሲ ነክ ጉዳዮችን ይፋ ማድረግ እንደማይጠበቅበት ገልጸዋል።

አክለውም የውጭ ምንዛሪን ስርዓቱን ገበያ መር እንዲሆን ማስቻልን ጨምሮ፤ ለባንኮች እንዲተገብሩት የተላለፈው ከ14 በመቶ በላይ የብድር ጣርያ ተያያዥ ጉዳዮችን አንስተዋል።

ንግድ ባንኮች እርስ በእርስ የሚበዳደሩበት ስርዓት መዘርጋቱ በኢኮኖሚ ማሻሻያ ከተደረገባውና አንዳንዶቹ አዲስ ያስተዋወቃቸው የገንዘብ ገበያ ስርዓቶች መሆናቸውንም ጠቅሰዋል።

በዚህ መሰረት ሁሉንም የመንግሥት ውሳኔዎች እወቁልን እያሉ በየጊዜው ማስተዋወቁን ብሔራዊ ባንክ አስፈላጊ ብሎ እንደሚያምንበት፤ የባንኩ የውጭ ምንዛሪ ቁጥጥር ስርዓት ምክትል ዳይሬክተሩ አበባየሁ ዱራፌ ሲናገሩ ሰምተናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በተደጋጋሚ የሚደረገውን የፖሊሲ ለውጥ ተከትሎ፤ "ገበያውን ከመጠበቅ አንፃር ጥንቃቄ የጎደላቸው ሕጎች እያወጣ ነው" በሚል ከፍተኛ ትችት ሲቀርብበት መቆየቱ የሚታወቅ ነው።

ይሁንና ባንኩ "የተሳኩ ውሳኔዎች አሳልፌያለሁ" የሚል እምነት እንዳለው ከዳይሬክተሩ መረዳት ተችሏል።

በሌላ በኩል አጠቃላይ የገንዘብ አስተዳደር ስርዓቱ ያለበትን አሁናዊ ሁኔታና የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ የተሳካ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።

በተለይም ሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ እንቅስቃሴዎች ለመግታት ያከናወናቸው ሥራዎች የተሳለጡና የተሳኩ እንደነበሩም ገልጸዋል።

አሁን ላይ ባንኩ በፍራንኮ ቫሉታ የወሰደውን እርምጃ ሕገወጥ የውጭ ምንዛሪ እንቅስቃሴ በፍጥነት የሚገታ ስልታዊ እርምጃ መሆኑን ተነግሯል።

የገንዘብ ሚኒስቴርና የጉምሩክ ኮሚሽን መስርያ ቤቶች ውሳኔውን ተፈፃሚ የሚያደርጉበትን ሁኔታ ለመተግበር የሚያስችሉ ስርዓቶች በመዘርጋት ረገድ እየተሰራበት መሆኑን ብሔራዊ ባንክ ገልጿል።

የባንኩ ውሳኔዎችም መለካት ያለባቸው በምጣኔ ሐብቱ በመጡት ተጨባጭ ውጤቶች መሆን እንደሚኖርበትም አቶ አበባየሁ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በአማኑዔል ክንደያ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 11:48


#አሐዱ_አብይ_ጉዳይ

ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/I657y-_k_YI?si=5BJAQbP9cRmWDbzg

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 09:36


በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከ60 በላይ መምህራኖች መታሰራቸውን ተገለጸ

ሕዳር 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ፤ 66 የሚደርሱ መምህራኖች "ደመወዝ ይከፈለን" የሚል በመጠየቃቸው ታስረዋል ሲል የኢትዮጵያ የመምህራን ማህበር አስታውቋል፡፡

የማህበሩ ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑቱ አቶ ሽመልስ አበበ፤ "መምህራኖቹ ደመወዝ ይከፈለን ብለው ስለጠየቁ ብቻ ለእስር ታዳርገዋል" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"በየትኛውም መልክ ደመወዝ መጠየቅ ለእስር ሊዳርግ አይችልም" ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ "ይህ አይነት ስርዓት አልበኝነት አካሄድ የትምህርት ስርዓቱን ለማደከም የታለም ነው" ሲሉ አውግዘዋል፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት መምህራንን ማሰር የጀመረው ከባለፈው ረቡዕ ጀምሮ መሆኑን ያስታወሱም ሲሆን፤ "ይህ አይነት መምህራንን የማሸማቀቅ አካሄድ ሊቆም ይገባል" በማለት አሳስበዋል፡፡

መምህራኖቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት በወረዳው ፖሊሶች እንደሆነ የተገለጸ ሲሆን፤ ከፍተኛ የሆነ ድብደባ ደርሶባቸው ለአካል ጉዳት የተዳጉም ሳይኖሩ እንዳልቀር የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

በውል የማይታወቁ መምህራን አሁንም የሕክምና እርዳታ የሚፈልጉ ቢሆንም፤ እርዳታ እንዲያገኙ በጸጥታ ሃይሎች ክልከላ እንደተደረገባቸው ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ የመምህራን ማህበር ምክትል ፕሬዝዳንት አክለውም፤ "ስልጣንም ያልፋል፣ ሁሉም ነገር ባለበት አይቀጥልም፣ ነገር ግን በተለይ ተደጋጋሚ የመምህራን ጥያቄ ማፈን ተቀባይነት የሌለው ጉዳይ ነው፡፡ በታሪክም የሚያስወቅስ ነው" ሲሉ ቅሬታቸውን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

መምህራኖቹ ተቃውሞ ያነሱት፤ በክልሉ መንግሥት ይሁንታ የ25 በመቶ የደመወዝ ቅነሳው ከትምህርት ቤት ርዕሰ መምህራን እና ሱፐርቫይዘሮች ላይ መደረጉን ተከትሎ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

በወረዳው 683 መምህራኖች እንዳሉ የተገመተ ቢሆንም፤ 66 የሚደርሱት መታሰራቸው ተገልጿል፡፡

በደረጄ መንግስቱ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 08:47


በሰሜን ሸዋ ዞን አለልቱ መንገድ ላይ ከባድ የትራፊክ አደጋ መከሰቱ ተሰማ

ሕዳር 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በዛሬው ዕለት በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አለልቱ መንገድ ላይ ከባድ የትራፊክ አደጋ መድረሱን አሐዱ የደረሰው መረጃ ያመለክታል፡፡

አደጋው አለልቱ አቅራቢያ ጮሌ ጸበል ጋር የተከሰተ ሲሆን፤ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ የሚጓዝ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከሲኖ ትራክ ተሸከርካሪ ጋር በመጋጨቱ መከሰቱን በስፍራው ያሉ ነዋሪዎች ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በአደጋው በርካታ ሰዎች መጎዳታቸውን እንዲሁም ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ሕይወት ማለፉን የተናገሩት ነዋሪዎቹ፤ የሲኖ ትራክ ተሸከርካሪው ረዳት መኪና ውስጥ ተቀርቅሮ በመቅረቱ እርሱን ለማውጣት ከአንድ ሰዓት በላይ ጥረት ቢደረግም ሕይወቱን ማትረፍ አለመቻሉን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ምክንያት መንገዱ ለእረጅም ሰዓት መዘጋቱ የተነገረ ሲሆን፤ በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች ወደሆስፒታል የማድረስ ሥራ እየተሰራ መሆኑም ተገልጿል፡፡

አደጋው ያደረሰውን ጉዳት መጠን አስመልክቶ፤ አሐዱ ዝርዝር መረጃ ባገኘበት ሰዓት ወደእናንተ ያደርሳል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

23 Nov, 07:03


"ተሃድሶ የሚወስዱት የቀድሞ ታጣቂዎች ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኃላ ያሉት ብቻ ናቸው" ብርጋዴር ጄነራል ደርቤ መኩሪያ

ሕዳር 14/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የቀድሞ ታዋጊዎች ሲባል ግርታ ውስጥ የመግባት ነገር መፈጠሩን የብሔራዊ ተሃድሶ ምክትል ኮሚሽነርና የመከላከያ ሠራዊት ተወካይ ብርጋዴር ጄነራል ደርቤ መኩሪያ ተናግረዋል፡፡

"ታጣቂዎችን የመለየቱ ሥራ በምን አግባብ ነው እየተሰራ ያለው?" የሚለው ሌላ ጥያቄ የሚያስነሳ መሆኑን የገለጹት ጄነራሉ፤ የተለያዩ ማረጋገጫዎችን መጠቀማቸውን ገልጸዋል፡፡

በዚህም "የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር እንደ ክልል ያለውን የተዋጊ ብዛት አሳውቋል" ያሉ ሲሆን፤ የሀገር መከላከያ ሚኒስቴርም ባለቤት በመሆኑ እንደ ሀገር ያለውን የታጠቀ አካላትን በመለየት ተከታትሎ ማስረጃ ማቅረቡን አስረድተዋል፡፡

ይህ ቁጥጥር የሚረጋገጠው ግን ተመዝግቦ ይፋ ሲደረግና መስፈርቶችን ሲያሟላ ብቻ መሆኑን የተገለጹ ሲሆን፤ "በስምምነቱ መሰረት ትጥቁን ያሰረከበ መሆን አለበት" ሲሉም ተናግረዋል፡፡

አንዳንድ ቦታ አሁንም የትጥቅ ትግል ውስጥ ያሉ ወገኖች መኖራቸውን ያነሱት ጀኔራል ደርቤ፤ ይህንን በሚመለከት ሌላ ኮሚሽን ሳያስፈልግ ባለው ኮሚሽን ተጠቅመው ወደ ትጥቅ መፍታት እንዲመጡ ጠይቀዋል፡፡

በዚህም በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ቤንሻንጉል፣ ትግራይ እና አፋር አካባቢ ላሉ ታጣቂዎች ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፤ በአፋር ክልል ከሰሞኑ ትጥቅ የማሰፈታት ሂደቶች መኖራቸውንም ተናግረዋል፡፡

የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን የጀመረው ትጥቅ የመፍታትና ወደ ማህበረሰብ የመቀላቀል ሥራ በትግራይ ክልል መቀሌ የተጀመረ ሲሆን፤ በመጀመሪያ ዙር 320 ታጣቂዎች ወደ ተሃድሶ ማዕከል መግባታቸው ተገልጿል፡፡

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 14:21


#አሐዱ_አብይ_ጉዳይ

ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/p8haUrt9HRQ?si=IwgR5874bU4qHy6B

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 12:42


ቢሮው ያለአግባብ ዋጋ የሚጨምሩ ነጋዴዎችን ለመቆጣጠር የምርቶችን ዋጋ በማህበራዊ ትስስር ገጹ ይፋ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ "የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች እንዲሁም የንግድ ማዕከላት የምርቶች ዋጋ ተመንን አላወጣም" በሚል የተጋነነ ዋጋ ጨምረው የሚሸጡ ነጋዴዎችን ለመቆጣጠር፤ በየማዕከላቱ የሚሸጡ ምርቶችን የዋጋ ተመን በየሳምንቱ ይፋ እንደሚያደርግ ገልጿል።

የቢሮው የገበያዎች ጥናት እና ማስታወቂያ ዳይሬክተር ሙሰማ ጀማል ለአሐዱ እንደገለጹት፤ በሳምንት ሦስት ቀናት በዋና የገበያ ስፍራዎች የምርቶችን ዋጋ ቅኝት በማድረግ በየሳምንቱ አርብ ከሰዓት በተቋሙ ማህበራዊ ትስስር ገጽ ላይ የምርቶችን የዋጋ ተመን ይገለጻል፡፡

"ይሄ አሰራር ማህበረሰቡ አስቀድሞ የምርቶቹን ዋጋ ስለሚያቃቸው በሕገወጥ ነጋዴዎች እንዳይጭበረበር ያደርገዋል" ብለዋል፡፡

አክለውም፤ ምርቶች እንደ ጥራታቸው የዋጋ ልዩነት እንዳላቸው አንስተው፤ ሁለተኛ ደረጃውን "አንደኛ ነው" እያሉ የሚሸጡ ነጋዴዎች መኖራቸውንም ተናግረዋል፡፡
በዚህ ረገድ ቢሮው አሰራሩ ከተጀመረ በኃላ ባልተገቡ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ በመወሰድ ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

260 በሚሆኑ ባለሙያዎች በገበያ ስፍራዎች የክትትልና የድጋፍ ሥራዎችን በሁለቱም ቀናት እንደሚሰጡ የተገለጸ ሲሆን፤ በአዲስ አበባ 193 የሚደርሱ የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች እንዲሁም 4 የገበያ ማዕከላት መኖራቸውንም አንስተዋል።

በዚህም መሰረት ንግድ ቢሮው፤ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የግብርና ምርቶች መሸጫ ከሕዳር 7 እስከ 13/2017 ዓ.ም እንዲሁም በዕሁድ ገበያዎች ዛሬ ሕዳር 7 እና ነገ 8/2017 ዓ.ም የሚቀርቡ የአትክልት፣ የፍራፍሬ፣ የሰብል ምርቶች እና የፋብሪካ ምርት ውጤቶች የመሸጫ ዋጋ መረጃ ይፋ አድርጓል፡፡

👉የመሸጫ ዋጋ ዝርዝሩ ከላይ ተያይዟል!

በፍርቱና ወልደአብ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 10:28


#አሐዱ_መድረክ

"ሕገ-መንግሥቱን የመተርጎም እንጂ የመሻሻል ስልጣን የለንም" ከሕገ-መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ ዋና ዳይሬክተር ደሳለኝ ወዬሳ ጋር የተደረገ ቆይታ (ክፍል 1)

ቆይታውን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
👇
https://youtu.be/_d9b5EF97ds?si=Aqyz0Jrbaitsrg3S

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 09:32


በአዲስ አበባ የሚያስተምሩ መምህራን ወቅታዊ የኑሮ ሁኔታ ከአቅም በላይ እንደሆነባቸው ተገለጸ

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ለመምህራን ይደረጋል የተባለውን የኑሮ ድጎማና የቤት አቅርቦት የውሃ ሽታ ሆኖል ሲል የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ተናግሯል።

ለመምህራን ይደረጋል የተባለውን ልዮ ጥቅማ ጥቅምን ጨምሮ፤ ቃል የተገባው የቤት አቅርቦት ተግባራዊ እንዲሆን ማህበሩ ጠይቋል።

ሀሳቡ የተነሳው ለሁለት ተከታታይ ቀናት ተከናውኖ በትናንትናው ዕለት በተጠናቀቀው፤ የአዲስ አበባ ከተማ መምህራን ማሕበር 37ኛ መደበኛ የምክር ቤት ጉባኤ ላይ ነው።

የማህበሩ የኮሙኒኬሽን ኃላፊ ሳሙኤል ሙሴ በጠቅላላ ጉባኤው በርካታ ጥያቄዎች እንደተነሱ ገልጸው፤ የኑሮ ውድነቱን ጨምሮ የቤትና ጥቅማ ጥቅሞች ጉዳይ በስፋት መነሳታቸውን ለአሐዱ ተናግረዋል።

አክለውም በአዲስ አበባ ያለውን የኑሮ ጫና በመምህራ ላይ እየበረታ መምጣቱን የገለጹ ሲሆን፤ ይህም በመማር ማስተማር ስርዓቱ ላይ ጫና እያሳደረ መምጣቱን ተናግረዋል።

የመምህራን ማሕበር ከዚህ ቀደም ያነሳቸው ጥያቄዎች መልስ እንዳልተሰጠባቸው የተገለጸ ሲሆን፤ የመምህራን ጥያቄ ቸል እየተባለ መሆኑንም ኃላፊው ጨምረው ለአሐዱ ገልጸዋል።

በአዲስ አበባ የሚገኙ መምህራን ህይወት አስቸጋሪ በሚባል ደረጃ ላይ መድረሱን በመጥቀስ፤ መፍትሔ እንዲሰጥበት መጠየቁን ተነግሯል።

የአዲስአበባ መምህራን ማሕበር በመጪዎቹ ጊዜያቶች የማሕበሩ ፕሬዚዳንት ምርጫ የሚያደርግ መሆኑንም ገልጿል።

በዚህ ጉባዔ የማጠቃለያ መድረክ ላይ የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ፣ የቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አሊ ከማል እንዲሁም ከከተማ ጀምሮ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ ያሉ የምክር ቤት አባላትና ሌሎች ከማህበሩ ጋር በጋራ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።

በአማኑዔል ክንደያ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 09:02


"የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሚያካሂደዉ ጉባኤ ሕገ-ወጥ በመሆኑ አንሳተፍም" ሲሉ 6 ፓርቲዎች ገለጹ

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)ን ጨምሮ ስድስት የሚሆኑ ፓርቲዎች ሕገ-ወጥ ያሉትን የኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ እንደማይሳተፉ ገልጸዋል።

ፓርቲዎቹ የጋራ ምክር ቤቱ ዛሬ ቅዳሜ ሕዳር 7 እና እሁድ ሕዳር 8/2017 ለማድረግ የጠራውን ጠቅላላ ጉባኤ እንዲሁም ሰብሳቢ፣ ምክትል ሰብሳቢ እና ሥራ አስፈፃሚ ለመመርጥ ማሰቡን በመቃወም ነው በጉባዔው እንደማይሳተፉ የገለጹት።

ግዜው የተጠናቀቀው የጋራ ምክር ቤቱ ምርጫ እና ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርግ ከዚህ ቀደም መጠየቃቸውን ያስታወሱት ፓርቲዎቹ፤ "ስብሰባ መጥራት አይችልም" ብለዋል።

በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)፣ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ)፣ የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ (ዎብን)፣ ህብር ኢትዮጵያ እና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ህብር- ኢትዮጵያ) ሕገ-ወጥ ነው ባሉት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንደማይሳተፉ ገልጸዋል።

በጉባኤው የሚወሰኑ ማንኛውም ውሳኔዎችንም እንደማይቀበሉም ፓርቲዎቹ አስታውቀዋል።

ምክር ቤቱ ጠቅላላ ጉባኤውን ያለፈው ነሐሴ ማድረግ ቢኖርበትም፤ በበርካታ ተቃውሞ ዛሬ ቅዳሜ እና እሁድ ያደርጋል።

ኢሕአፓን ጨምሮ ስድስት ፓርቲዎች ከዚህ ቀደም ጠቅላላ ጉባኤ እንዲደረግና ምርጫ እንዲደረግ መጠየቃቸው አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል።

ፓርቲዎቹ በዚህ ጉዳይ ላይም ቀጣይ እርምጃዎችን በተመለከተ በቅርቡ እንደሚያሳውቁም ገልጸዋል።

የኢትዩጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በበጀት እጥረት ጉባኤዉን አለማካሄዱን መዘገባችን ይታወሳል።

በአቤል ደጀኔ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 08:29


"ቴክኖሎጂን በመጠቀም በሰዓታት ውስጥ የስኳር በሽታን ማጥፋት ተችሏል በሚል የተሰራጨው መረጃ ከእዉነት የራቀና አሳሳች ነዉ" ጤና ሚኒስቴር

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከሰሞኑ ቴክኖሎጂን በመጠቀም በሰዓታት ውስጥ የስኳር በሽታን ማጥፋት ተችሏል በሚል እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ ከእዉነት የራቀና አሳሳች ነዉ ሲል ጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛዎች የስኳር ሕመምን ጨምሮ ሃሰተኛ የጤና መረጃዎች ኃላፊነት በጎደላቸው አካላት እየተለቀቁ እንደሚገኝ ገልጿል።

አክሎም የሕክምና ሙያ ሳይኖራቸውና ለሚሠጡት አገልግሎት ሕጋዊ የሆነ የብቃት ማረጋገጫ ሳይኖራቸው በማህበራዊ ሚዲያ ማህበረሰቡን የሚጎዱ፣ ከእውነት የራቁ ሀሰተኛ መረጃዎችን የሚለቁ አካላት መበራከታቸውን አስታውቋል።

ይህ ተግባር ማህበረሰቡን በእጅጉ እየጎዳና ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት ከመዳረግ አልፎ፤ ፈውስ ፈላጊ ዜጎች ላይ ከፍተኛና የተወሳሰበ የጤና ችግር እየፈጠረ እንደሚገኝም ገልጿል።

ስለሆነም በዚህ መሰል ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አካላት ይህ ተግባር በሕግ የሚያስጠይቅ መሆኑን ተገንዝበው፤ ከእኩይ ተግባራቸው እንዲታቀቡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል፡፡

ማህበረሰቡም ምንጫቸው ካልተረጋገጠ አካላት የሚላኩ መልእክቶችን እንዲመረምር፣ አገልግሎቶችንም ከመጠቀማችን በፊት ጥንቃቄ እንድናደርግ፣ አስፋላጊ ሆኖ ሲገኝም በ"[email protected]" ላይ ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል፡፡

ሕዝቡ ሀሰተኛ የጤና መረጃ የሚለቁትን በማጋለጥ፣ የጤና ባለሙያ በማማከር ጤንነቱን እንዲጠብቅም ጤና ሚኒስቴር አሳስቧል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 08:03


የአክስዮን ሽያጭ የሚሰሩ ደላሎችን በታሰበው ልክ ማግኘት እየተቻለ አለመሆኑ ተገለጸ

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በድለላ ሥራ የሚሳተፉ ድርጅቶችና ግለሰቦች ለመመዝገብ ተደጋጋሚ ጥሪ እየተደረገ ቢሆንም፤ በታቀደው ልክ እየተገኙ እንዳልሆነ የኢትዮጵያ የሰነድ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ መስርያ ቤት የኦፕሬሽን ኃላፊ አቶ ሚኪኤል ሐብቴ ለአሐዱ ገልጸዋል።

ኃላፊው "የኢትዮጵያ አክስዮን ገበያ መከፈቱን ተከትሎ ገበያው በታቀደለት መልኩ እንዲተገበር በድለላ ሥራ የሚሳተፉ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑን ሲገለጽ የቆየ ቢሆንም፤ በታለመለት መልኩ እየተጓዘ አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የመዋእለ ሰነድ ግብይት በተሳካ መልኩ እንዲሳለጥ በዋነኝነት የድለላ ሥራ የሚሰሩ አካላት በስርአቱ መሳተፍ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

ነገር ግን ከታሰቡት ደላሎች ውስጥ፤ አሁን ላይ የተመዘገቡት በቁጥር አነስተኛ ናቸው ብለዋል።

ለዚህም እቅዱ ላይ ተግዳሮት እንደሆነ የተናገሩ ሲሆን፤ "አሁንም አቅሙ ያላቸው አካላት እንዲመዘገቡ ጥሪ ይደረጋል" ብለዋል።

በታሰበው ልክ ደላሎች የማይገኙ ከሆነም ዘርፉን የሚያከናውኑ አካላትን ጨምሮ ተገበያዮች የሚገናኙበት አማራጭ እንደሚፈለግለት አቶ ሚኪኤል ለአሐዱ ገልጸዋል።

የድለላ ሥራን የሚሰሩ ድርጅቶች አስፈላጊነት በተደጋጋሚ ሲነገር የቆየ ጉዳይ ቢሆንም፤ እንደ አገር ካለው ግንዛቤ አንፃር በታቀደው ልክ ማግኘት እየተቻለ አለመሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዚህም መሰረት ኢትዮጵያ የከፈተችው የአክስዮን ገበያ በተሳካ መልኩ እንዲጓዝ፤ እነዚህ ደላሎች ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ዘርፉን ለማነቃቃት በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ቢሆንም፤ ከግንዛቤ ውስንነት አንፃር ተግዳሮት እንደገጠመው መስርያ ቤቱ ተናግሯል።

የኢትዮጵያ ሰነድ መዋእሎ ንዋዮች አክስዮን ገበያ ለማሻሻጥ የተቋቋመ መስርያ ቤት መሆኑን ይታወቃል።

በአማኑዔል ክንደያ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 07:42


የኢትዮጵያ አየር መንገድ 'ምርጥ የአፍሪካ ካርጎ አየር መንገድ' ሽልማትን ተሸለመ

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ለሁለተኛ ተከታታይ ግዜ በ “Arabian Cargo Awards” ምርጥ የአፍሪካ ካርጎ አየር መንገድ ሽልማትን ተቀዳጅቷል።

የሽልማት አሰጣጥ መርሐግብሩ በዱባይ ከተማ የተካሄደ ሲሆን፤ በገልፍ ሀገራት ለሚሰጡ ምርጥ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎቶች ዕውቅና የሚሰጥበት መድረክ መሆኑን አየር መንገዱ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ትናንት ሕዳር 6/2017 ዓ.ም የ2024 የቢዝነስ ተጓዦች ሽልማት ውድድርን በማሸነፍ፤ ለአምስተኛ ተከታታይ ዓመት ‘ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ’ በመባል መሸለሙን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 07:15


የድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና ከ 30 ሺሕ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ እድል እንደሚፈጥር ተገለጸ

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከቀናት በፊት ወደ ትግበራ የገባው የድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና ከ30 ሺሕ በላይ ለሆኑ ዜጎች ቀጥተኛ የሥራ እድልን እንደሚፈጥር፤ የድሬዳዋ ነፃ ንግድ ቀጠና ልዩ ኢኮኖሚ ዞን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አህመድ ረሺድ ለአሐዱ ገልጸዋል።

ከ200 በላይ ባለሀብት ወደ ከተማዋ ይገባል ተብሎ እንደሚጠበቅ የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ "ሁሉም የሚገቡ ከሆነ አጠቃላይ የኢትዮጵያን የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) 3 በመቶ ይሸፍናል" ሲሉም አክለዋል።

"ነፃ የንግድ ቀጠናው በድሬዳዋ የተመሰረተው ከተማዋ ለበርበራና ጅቡቲ ወደብ ቅርበት ያላት ከተማ በመሆንዋ ነው" ያሉም ሲሆን፤ በዋናነት ግን ከሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች በተሻለ መልኩ ድሬዳዋ ውስጥ አንፃራዊ ሰላም መኖሩና የከተማው አመሰራረት ንግድ ላይ የተመሰረተ በመሆኑ ነው" ብለዋል።

የንግድ ትግበራዉ መጀመር የውጭ ምንዛሬ ወጪን የሚቀንስና የገቢና ወጪ ንግድን በፍጥነት የሚያሳልጥ ስለመሆኑም አስረድተዋል፡፡

በነፃ ንግድ ቀጠናው የሚሰጡ አገልግሎቶች በዋናነት ንግድ፣ ሎጀስቲክስ እና ማኑፋክቸሪንግ መሆናቸዉን በመግለጽ፤ አጠቃላይ ክንውኑም 70 በመቶ ንግድ፣ 30 በመቶ ደግሞ ማኑፋክቸሪንግ መሆኑን ተናግረዋል።

ነፃ ንግድ ቀጠናው ውስጥ የትኛውም ኢንቨስተር ይዞት የመጣውን ገንዘብ መቶ በመቶ መጠቀም እንደሚችል ተገልጿል።

ምርት ከውጪ ወደ ሀገር ውስጥ በሚገባበት ሰዓት ከተለመደው የንግድ አሰራር በተለየ መልኩ ባለሀብቱ አንዴ ፈቃድ አግኝቶ ሥራ ሲጀምር፤ ምንም አይነት የባንክ ፈቃድና ቀረጥ መክፈል ሳይጠበቅበት የሚያስገባበት አሰራር መኖሩንም ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ አህመድ አመላክተዋል፡፡

"ከሚልኩበት ሀገር ወደ ድሬዳዋ ዶክመንት ብቻ በመላክ ፍተሻ ሳይደረግበት በቀጥታ እቃውን ማራገፍ ይችላል" ሲሉም አክለዋል።

ለምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ እንዳይላሉ ሰሎሞን በበኩላቸዉ፤ "ነፃ የንግድ ቀጠናው ድሬዳዋ መጀመሩ በዋናነት ድሬዳዋ ከወደብ ሀገራት ጋር ቅርበት ስላላት መሆኑን መልካም የሚባል ነው" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ነፃ የንግድ ቀጠናው ለኢኮኖሚው መነቃቃትና እድገት ዘርፈ ብዙ አስተዋጽኦ እንዳለው ገልጸው፤ "ነገር ግን ይህ ሁሉ ሊሰራ የሚችለው የአሰራር ስርዓቱ አመቺ ሲሆን ነው" ብለዋል፡፡

በስፍራሽ ደመላሽ
#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

16 Nov, 06:24


በኦሮሚያ ክልል በሕገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ 13 ሚሊዮን ብር የሚገመት ነዳጅ መያዙ ተገለጸ

ሕዳር 7/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኦሮሚያ ክልል በ4 ወር ጊዜ ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ 13 ሚሊዮን ብር የሚገመት ነዳጅ መያዙን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡

በክልሉ ሕገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን በተመለከተ ቁጥጥርና ክትትል በማድረግ ሕገ ወጥ ነዳጁ ሲዘዋወር በቁጥጥር ሥር መዋሉን፤ የክልሉ ንግድ ቢሮ የእንስፔክሽን ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ጉዲሳ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

ከዚህም ውስጥ 1 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር የሚገመት ነዳጅ ለመንግሥት ገቢ መደረጉን ገልጸው፤ ቀሪው ደግሞ በሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ የሚስተዋለውን የሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ለማስቆም፤ በተለያዩ ዞኖች እና ከተሞች ላይ ቁጥጥርና ክትትል እየተደረገ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡

የነዳጅ ግብይትን በተመለከተ በሕጋዊ መንገድ አገልግሎቱ እንዲሰጥ የማድረግ ሥራ እየተሰራ መሆኑንም ኃላፊው ተናግረዋል፡፡

ነዳጅ ከቦታ ቦታ በማዘዋወር እንዲሁም በሕገ-ወጥ መንገድ በመሸጥ ላይ የተገኙ ግለሰቦች የያዙት ነዳጅ እንደሚወረስ የጠቆሙም ሲሆን፤ በተጨማሪም አስተዳደራዊ እርምጃና የጹሁፍ ማስጠንቀቂያ በመስጠት እርምት የማስወሰድ ሥራ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡

ቢሮው በሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ ላይ የሚንቀሳቀሱ ሰዎችን ለመቆጣጠር ከሚመለከተው አካል ጋር እየሰራ መሆኑንና ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመስጠት ጥቆማ እንዲያደርጉ እየተሰራ ስለመሆኑም አቶ ጌታቸው ጨምረው አመላክተዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 15:30


#አሐዱ_መድረክ

"በአማራ ክልል ግጭት ሳይሆን ጦርነት ነው እየተካሄደ ያለው" (ክፍል 2)

ሙሉ ቆይታውን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
👇
https://youtu.be/OACq3rvp0Ik?si=liVFbo4f9avBaXYG

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 12:00


በኦንላይን የሚፈጠሩ ማጭበርበሮችን መቆጣጠር አስቸጋሪ እንደሆነበት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ

ጥቅምት 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በስልክ እየደወሉ እንዲሁም የተለያዩ የኦን ላይን ዘዴዎችን ተጠቅመው ከደንበኞች ላይ የሚያጭበረብሩ ግለሰቦችን አግኝቶ እርምጃ ለመውሰድ አስቸጋሪ እንደሆነበት ገልጿል፡፡

የተፈጠረው ችግር በራሱ በደንበኛው ነው ውይንስ በሌላ አካል ነው የሚለውን ለመለየት የሚያስቸግር በመሆኑ፤ በህግ ለማስጠየቅም ከፍተኛ ችግር እየፈጠረበት መሆኑን ነው ያስታወቀው፡፡

በዚሁ ዙሪያ ለሚፈጠሩ የኦን ላይን ማጭበርበሮች ጥፋት ተጠያቂ ለማድረግ በኢትዮጵያ ሕግ ባለመኖሩም ችግር እየፈጠረ መሆኑ ተነስቷል።

"በመሆኑም ይህንን በሚመለከት ከህግ አውጪዎች ጋር ውይይት በማድረግ በህግ ማዕቀፍ ለማስገባት እየተሰራ ነው" ሲሉ አሐዱ ያነጋገራቸው የባንኩ የኢንፎርሜሽን ሲስትም ምክትል ፕሬዝደንት አቶ አማረ አሰፋ ተናግረዋል፡፡

ባንኩ ከፖሊስ እና ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ጋር በመሆን መረጃዎችን ተንትኖ አጥፊዎችን ለማጋለጥ እየሰራ እንደሆነም ጨምረው ተናግረዋል፡፡

በአብዛኛው የሚፈጠሩ ወንጀሎች የሚፈፀሙት ደንበኛው ካለው የመረጃ እጥረት የተነሳ በመሆኑ ይህንን ችግር ለመፍታት በርካታ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየሰራን እንገኛለን ሲሉም አቶ አማረ ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

በአቤል ደጀኔ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 11:55


የጥብቅና ሙያ እንደማንኛውም የንግድ ሥራ መታየት የለበትም ሲል የፌደራል ጠበቆች ማህበር ተናገረ

ጥቅምት 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የፌደራል ጠበቆች ማህበር የጠበቃነት ሙያ ከፍትሕ ስርአቱ ጋር የሚገናኝ ጉዳይ በመሆኑ፤ ሙያው እንደ ሌላው የንግድ አይነት መታየት እንደሌለበት ለአሐዱ ገልጿል።

በኢትዮጵያ ንግድ ሕግ መሰረትም ሙያው እንደሌላው የንግድ አይነት መታየት እንደሌለበት ቢደነግግም፤ በሥራ ላይ ግን በተቃራኒው እየተተገበረ እንደሚገኝ የማሕበሩ ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ጌታቸው ለአሐዱ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸው፣ በተለያዩ አገራት ያለውን ልምድ ጠቅሰው ለጥብቅና ሙያ የሚሰጠው ከለላና የሙያው ጠርዝ እንዲከለል በማድረግ ረገድ በኢትዮጵያ ካለው የተለየ ነው ብለዋል።

አሐዱም ለጥብቅና ሙያ በልዩነት እንደሌላው ንግድ መታየት የለበትም የሚለውን የማሕበሩ ቅሬታ በማንሳት የማሕበሩን ፕሬዝዳንት የጠየቀ ሲሆን፤ በምላሻቸውም በኢትዮጵያ ያለው የንግድ ሕጉ ጭምር ቀደም ሲል እንደማይፈቅድ ተናግረዋል።

የጥብቅና ሙያ ከሌላው የንግድ አይነት በተለየ መልኩ ምርትና አገልግሎትን ማስተዋወቅ በንግድ ሕጉ የተከለከለ መሆኑንም ገልጸዋል።

ይህ በእዲህ እንዳለ ንግድ ሥራ ፍቃድ በሚስጥበት ጊዜም ጠበቆች ማሕበራዊ ግልጋሎት እንዲሰጡ የሚያስገድድ አንቀጽ እንዳለው አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የጠበቆች ግብር ክፍያን በተመለከተ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተደጋጋሚ ቅሬታ ሲነሳበት እየተሰማ ነው ተብሏል።

ይሁንና ከዛሬ ነገ መፍትሔ ያገኛል ተብሎ እየተጠባበቁ እንደሆነ በመግለጽም፤ የሚመለከተው አካል ጉዳዮን በትኩረት እንዲመለከተው መጠየቁ ተነግሯል።

የገቢዎች ሚኒስተርና በበኩሉ በጉዳዩ ላይ ከሚመለከታቸው አካላት ማለትም የገንዘብ ሚኒስቴርና የፍትሕ ሚኒስቴር ጋር እየተመከረበት መሆኑን ገልጿል።

በቅርቡም መፍትሔ ያገኛሉ የሚል እምነት እንዳለው ጠቅሶ፤ በዋነኝነት ጉዳዩ ኢትዮጵያ በምትመራበት የንግድ ሕግ አንፃር የሚታይ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር መናገሩን ይታወሳል።

በአማኑዔል ክንደያ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 10:34


#አሐዱ_መድረክ

"ፓርላማ ላይ መልስ መስጠት ለሀገር ሰላም አያስገኝም"

ሙሉ ቆይታውን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
👇
https://youtu.be/exin1vDw-Ss?si=uCqWfGtmlIq3oZ-P

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 10:25


አሐዱ ባንክ የጸጥታ ችግር እና የኢኮኖሚ አለመመጣጠን ከፍተኛ ተጽዕኖ እንዳሳደረበት ገለጸ

ጥቅምት 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አሐዱ ባንክ በአገልግሎት ዘርፍ በአለም አቀፍ ደረጃ በሚታየው ምቹ ያልሆነ የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ በአንዳንድ የሐገሪቱ ክፍሎች የሚስተዋሉት የጸጥታ ችግሮችና የኢኮኖሚ አለመመጣጠን ጋር ተደማምሮ በከፍተኛ ሁኔታ ተጽዕኖ እንዳደረሰበት አስታውቋል፡፡

ባንኩ በዛሬው ዕለት 3ኛ መደበኛ የባለ አክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤውን በሚሊኒየም አዳራሽ አከናውኗል፡፡

በጉባዔውም የባንኩ ዘርፍ ተለዋዋጭና ጥብቅ በሆነ መመሪያዎች ውስጥ እንደሚንቀሳቀስ የገለጹት የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ አቶ አንተነህ ሰብስቤ፤ ለማሳያነት በነሐሴ 2016 የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የናረውን የዋጋ ግሽበት ለመቆጣጠር በማለም የንግድ ባንኮች በሚያበድሩት ብድር ላይ ጣሪያ ማስቀመጡን አስታውቀዋል፡፡

ይህ ፖሊሲ በባንኮቹ አፈጻጸምና በኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች እንዲሁም በሐብት ማንቀሳቀስ አቅም ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳደረ እንደነበረ ጠቅሰዋል፡፡

አክለውም፤ ይህንን ፈታኝ ተግዳሮት በማለፍ በተቋቋመ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጥሩ የሚባል ትርፍ ማስመዝገብ መቻሉና የበጀት ዓመቱን በስኬት ማጠናቀቁን አቶ አንተነህ ተናግረዋል፡፡

የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ በሪፖርታቸው ፤ አሐዱ ባንክ በዋና የፋይናንስ መለኪያዎች እድገት በማስመዝገብ የሚያስመሰግን ውጤት ማግኘቱን ገልጸዋል፡፡
የባንኩ ቅርንጫፍ ተደራሽነትን ወደ 104 ከፍ ማድረግ መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

በውጭ ምንዛሬ ረገድም 80 ነጥብ 1 ቢሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ የፋይናንስ ሁኔታ የተሻሻለ እንደነበር በመግለጽ በአሁኑ ወቅት የባንኩ አጠቃላይ ሐብት 6 ነጥብ 26ቢሊዮን መድረሱን አንስተዋል፡፡

የባንኩ የተፈጸመ የካፒታል መጠን ብር 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን መሆኑን አንስተው፤ አጠቃላይ የተከፈለ 1 ነጥብ 03 ቢሊዮን ማድረስ መቻሉንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በቀጣይ ዓመት የሀገሪቷን የሚኒተሪ ፖሊሲ ለውጦችን በመከተል ተከታታይ ጥናቶችን በማካሔድ ከወቅቱ ጋር በተመጣጣነ መልኩ እንደሚሰሩ አመላክተዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 09:57


ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ውል ለማቋረጥ የተሰጠው ማስጠንቀቂያ እስከ ሕዳር 30 ተራዘመ

ጥቅምት 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተለያዩ ጊዜያት በእጣ እና በጨረታ ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ውል ለማቋረጥ የሰጠውን ማስጠንቀቂያ እስከ ሕዳር 30 ቀን 2017 ድረስ ማራዘሙ አስታውቋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የቤት ባለቤቶቹ ወደ ቤታቸው የማይገቡ ከሆነ በሕግ አግባብ ውል የሚቋረጥ መሆኑን ማስጠንቀቁ ይታወሳል፡፡

በዚሁ አግባብ በርካታ የቤት ባለቤቶች ወደ ቤታቸው የገቡ ወይም ለመግባት ዕድሳት ላይ ስለመሆናቸው ባደረገው የአካል ምልከታ መገንዘቡን የገለጸ ሲሆን፤ አሁንም አንዳንድ የቤት ባለቤቶች ወደ ቤታቸው ለመግባት ምንም እንቅስቃሴ ያላደረጉ በመሆኑ በውል ተላልፈው ነዋሪ ያልገባባቸው ቤቶች እንዳሉ መለየቱን አመላክቷል፡፡

በመሆኑም የኮርፖሬሽኑን ጥሪ ተቀብለው ቤታቸውን አድሰው ለመግባት የጊዜ እጥረት ያጋጠማቸው አንዳንድ የቤት ባለቤቶች ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት የተሰጠውን የጊዜ ገደብ ማራዘም አስፈላጊ መሆኑ እንደታመነበት ገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት እስካሁን ድረስ ወደቤታቸው ለመግባት ምንም አይነት እንቅስቃሴ ያላደረጉ እንዲሁም ቤት ለማደስ የጊዜ እጥረት ያጋጠማቸው የቤት ባለቤቶች እስከ ሕዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ቤታቸው እንዲገቡ ለመጨራሻ ጊዜ ጥሪ አስተላልፏል፡፡

በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ የማይገቡ ነዋሪዎች የሽያጭ ውላቸው የሚቋረጥ እና በቤታቸው ውስጥ ለሚፈጸም ማንኛውም ሕገወጥ ድርጊት ተጠያቂ የሚሆኑ መሆኑንም ኮርፖሬሽኑ በጥብቅ አሳስቧል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 09:24


የቱሪዝም ሚኒስቴር ላለፋት 15 ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን ፓሊሲ ማሻሻያ ሊያደርግ መሆኑን ገለጸ

ጥቅምት 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የቱሪዝም ሚኒስቴር ከተለያዩ ሀገራዊና ዓለም አቀፍ ለውጦችን ከዘርፉ ፍላጎት ጋር ለማጣጣም በማለም ላለፋት 15 ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን ፓሊሲ ማሻሻያ ሊያደርግበት መሆኑን አስታውቋል፡፡

ሚኒስቴሩ የቱሪዝም ፓሊሲውን ክለሳ በተመለከተ ከግሉ ዘርፍ እና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተወካዮች ጋር ምክክር አድርጓል።

የኮሮና ወረርሽኝ፣ የሰሜኑ ጦርነት፣ የቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር ያለው ተወዳዳሪነት እና ፓሊሲው የቀደመው ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴርን መሠረት ያደረገ መሆኑ ፓሊሲውን ለመከለስ ምክንያት እንደሆነ የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ስለሺ ግርማ ገልጸዋል።

ይህ ፓሊሲ ከ2001 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 15 ዓመታት ሲያገለግል መቆየቱን አንስተዋል። "ፓሊሲውን ተግባራዊ በማድረግ ሂደትም ካለፉት 15 ዓመታት ወዲህ ብቁ የሠው ሀይል በመኖሩ መልካም አጋጣሚ ነው" ብለዋል።

እንዲሁም በግል ዘርፍ የተሠማሩ ባለሀብቶችም ተሳታፊ መሆናቸውና በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተገነቡ ያሉ የቱሪዝም መዳረሻዎች መስፋፋታቸውን ገልጸዋል።

አሁን በሥራ ላይ ያለው ፓሊሲ የራሱ የሆኑ በጎና አሉታዊ ጎኖች አሉት የተባለ ሲሆን፤ ፓሊሲው የሚፈለገው ግብዓቶች ከተካተቱበት በኋላ ለፕላንና ልማት ሚኒስቴር እንዲሁም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሚቀርብ መሆኑን ዶ/ር የዚህዓለም ሲሳይ ተናግረዋል።

"ፓሊሲው ድህነትን በማስወገድ፣ ባህላዊና ማህበራዊ ሁነቶችን በመጠበቅ ረገድ የራሱን ሚና ቢጫወትም የጎብኚዎች ቁጥር በሚፈለገው ልክ አለመጨመር፣ መዳረሻዎችን ለማስፋት ውስንነት እና አለም ከቀፍ ተደራሽነት ዝቅተኛ ነበር" ብለዋል።

በተመሳሳይም የቴክኖሎጂ፣ የቅርስ ጥበቃ፣ የአደጋ እና ቅድመ መከላከል አማራጭ መንገዶች ፓሊሲዉ ያልተመለከታቸው እንዲሁም ግልጽ መመሪያዎችን ያላስቀመጠ መሆኑን ገልጸዋል።

በሚከለሰው አዲሱ ፖሊሲ ሰፊ የሥራ እድል የውጭ ምንዛሬ ኢንቨስትመንትን ማበረታታት የአገልግሎት ጥራት ቅርሶቸን በአግባቡ መጠበቅ እንዲሁም የአፈጻጸም ክፈተቶችን ለመሙላት አቅጣጫዎችን ማስቀመጥ ጨምሮ የሚመለከት እንደሚሆን አንስተዋል።

በፍርቱና ወልደአብ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 08:21


ወጋገን ባንክ በበጀት ዓመቱ ትርፍ በትርፍ ሆኟለሁ አለ

ጥቅምት 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ወጋገን ባንክ በበጀት ዓመቱ 9 ነጥብ 8 ቢልየን ብር የተጣራ ገቢ ማግኘቱን ለአክስዮን ባለ ድርሻዎች እወቁልኝ ብሏል።

ባንኩ በበጀት ዓመቱ ያገኘው ትርፍ ካለፉት በጀት ዓመታት ከፍተኛው ትርፍ መሆኑን በዛሬው ዕለት ባካሄደው የባለአክስዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ገልጿል።

ባንኩ በበጀት ዓመቱ ያገኘው ትርፍ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲመሳከር በ40 በመቶ ብልጫ እንዳለውም ገልጿል።

ባንኩ ያገኘው ትርፍ በታሪኩ ከፍተኛውን መሆኑን ጠቅሶ፤ የትርፍ መጠኑንና የአክስዮን አባላቱ ቁጥር እያደገ መሆኑን ተናግሯል።

የአንድ አክስዮን ትርፉ ወደ 36 ነጥብ 9 በመቶ አድጎለታል ተብሏል።

የባንኩ የተከፈለ ካፒታል 27 በመቶ እድገት ማሳየቱንና በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 5 ነጥብ 1 ቢልየን ብር መድረሱን የገለጸ ሲሆን፤ ይህም ብሔራዊ ባንክ ለባንኮች ካስቀመጠው የባንኮች አነስተኛ ካፒታል መስፈርት በላይ መሆኑን ለአክስዮን ባለድርሻዎች አስታውቋል።

በበጀት ዓመቱ የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘብ የ22 በመቶ እድገት በማስመዝገብ 52 ነጥብ 1 ቢልየን ብር መድረሱንም ጠቅሷል።

ባለአክስዮኖች ብዛትም በ12 ሺሕ ያህል እንዳደገለት የገለጸም ሲሆን፤ ባንኩ ከዚህ ቀደም የገጠሙትን ችግሮች በመቅረፍ ወደ ተሻለ ደረጃ የትርፍ መጠኑን ማድረሱን ገልጿል።

በአማኑዔል ክንደያ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

09 Nov, 08:11


መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን ከ2 ሺሕ በላይ ተማሪዎች አስመረቀ

ጥቅምት 30/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ፣ በሁለተኛ እና በሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት መርሃ ግብሮች ያሰለጠናቸውን 2 ሺሕ 811 ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በሀውልቲ ሰማዕታት አዳራሽ አስመርቋል።

ዩኒቨርሲቲው ያስመረቀው በህክምና፣ በምህንድስና፣ በተፈጥሮ ሳይንስ እና በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ተማሪዎችን ሲሆን፤ 1 ሺሕ 950ዎቹ በመጀመሪያ ዲግሪ ቀሪዎቹ ደግሞ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

በተጨማሪም ዩንቨርስቲው ካስመረቃቸው ተማሪዎች መካከል 28 በመቶዎቹ ሴት ተማሪዎች መሆናቸው ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይም የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ የተመራቂ ተማሪዎች ቤተሰቦች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ከድህረ ጦርነቱ በኃላ ለሁለተኛ ጊዜ ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን፤ ዘንድሮ በአንደኛ፣ በሁለተኛና በሦስተኛ ዲግሪ የትምህርት መርሃ ግብር ተማሪዎቹን ሲያስመርቅ ይህ ለ30ኛ ጊዜ ነው፡፡

በዘንድሮ የትምህርት ዓመት 2 ሺሕ 800 አዳዲስ ተማሪዎች ወደ ዩንቨርስቲዉ የተመደቡ ሲሆን፤ በመጪው ጥር ወር አዲስ ለተመደቡ ተማሪዎቹች ጥሪ የማድረግ እንቅስቃሴ እንደሚጀመር ተገልጿል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 14:39


#አሐዱ_ትንታኔ

ሄዝቦላህ ለመጀመሪያ ጊዜ በቴልቪቭ የሚገኘው የእስራኤል ጦር ሰፍር በሰው አለባ ድሮን መደብደብ መጀመሩን አስታውቋል። የሊባኖሱ ታጣቂ ቡድን ሄዝቦላህ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በቴላቪቭ የሚገኘውን የእስራኤል ግዙፍ የጦር ሰፍር መደብደቡንም ገልጿል፡፡

የቡድኑ ጥቃት ከእስራኤል የአየር መከላከያ "አይረደም"  ቁጥጥር ውጭ ሊሆን እንደሚችል ስጋት ፈጥሯል። ጥቃቱን አስመልክታ እስራኤል ምላሽ ሰጥታለች፡፡ እነዚህን እና ተያያዥ ጉዳዮችን በዛሬው የአለም አቀፍ ትንታኔያችን ተመልክተነዋል፡፡

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/MVu7_16OyU0?si=d9r6Nbly6VDrxn-0

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 13:59


በጠበቆች ላይ እየተጣለ ያለውን የግብር አከፋፈል ቅሬታ የሚከታተል ኮሚቴ መቋቋሙ ተገለጸ

ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከዚህ በፊት በጠበቆች ላይ በሚጣለው ግብር ቅሬታ እንዳለ ሲገልጽ የቆየ ሲሆን፤ የፌደራል ጠበቆች ማሕበር አሁን ላይ የቀረቡ ቅሬታዎችን የሚከታተል ኮሚቴ መቋቋሙን ገልጿል።

የተቋቋመው ኮሚቴ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው የመንግሥት መስርያ ቤቶች የተውጣጡ አባላትን የያዘ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

በዚህም በጠበቆች ላይ እየተጣለ ካለው ግብር ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጥያቄ እልባት ያገኛል የሚል እምነት መኖሩን፤ የፌደራል ጠበቆች ማሕበር ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ጌታቸው ለአሐዱ ገልጸዋል።

ማሕበሩ በተለያዩ ጊዜያቶች ጥያቄውን ሲያቀርብ የነበረ ቢሆንም ከመንግሥት ትኩረት ተነፍጎት መቆየቱን ነው ፕሬዝዳንቱ የተናገሩት።

የጥብቅና ሥራ ከፍትህ ስርአቱ ጋር የሚገናኝ መሆኑን ጠቅሰው፤ እንደ አገር ጥሩ የሚባል ልምምድ እንዳልሆነም ጠቁመዋል።

እየቀረበ ያለውን ጥያቄ የገቢዎች ሚኒስቴርን ጨምሮ የፍትሕ ሚኒስቴር ጉዳዩን እንዲያጤኑ ማሕበሩ ሐሳብ ማቅረቡንም ፕሬዝዳንቱ አክለው ተናግረዋል፡፡

ማሕበሩ እንዲህ ያለውን ጥያቄ ማቅረብ ከጀመረ ከሁለት ዓመታት በላይ እንደሆነው የገለጸም ሲሆን፤ ይሁን እንጂ እስካሁን ከመንግሥት የተሰጠ አጥጋቢ ምላሽ ማግኘት እንዳልቻለ አስታውቋል።

በአማኑዔል ክንደያ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 12:59


በአማራና ኦሮሚያ ክልል ያለው ማህበረሰብ በመንግሥትና ታጣቂ ሃይሎች መካከል ሆኖ ዋጋ እየከፈለ ነው ሲሉ ፓርቲዎች ገለጹ

ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአማራና እና ኦሮሚያ ክልል በመንግሥት ሃይሎች እና በታጣቂዎች መካከል ባለው ግጭት ህብረተሰቡ ዋጋ እየከፈለ ነው ሲሉ ከአሐዱ መድረክ ጋር ቆይታ ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ገልጸዋል።

" 'የቀን ገዢና የማታ ገዢ' በሚል ህብረተሰቡ እየሞተ ነው" ያሉት ፖለቲከኛና የእናት ፓርቲ አባል የሆኑት ጌትነት ወርቁ፤ "በተለይም በኦሮሚያ ክልል ችግሩ የጎላ ነው" ይላሉ።

"በተመሳሳይም በአማራ ክልል የተሟላ ጦርነት እየተካሄደ ነው" ያሉ ሲሆን፤ በመጠኑና በአይነቱ ከሌሎች ጦርነቶች የሚለየበት ሁኔታ ስለመኖሩም ተናግረዋል።

"በሁለቱም ክልሎች ያለው ሁኔታ የሚገለፅበት መንገድ የተለያየ ቢሆንም፤ የመፍትሔ ሃሳቦች ግን ሁሉንም ሊያስማሙ ይችላሉ" ያሉት ፖለቲከኛ ጌትነት፤ በእነዚህ ክልሎች የተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ ዜጎች በከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደሚገኙም አንስተዋል።

"መንግሥት 'አደረኩ' ያላቸው ጥረቶች የሚበረታቱ ቢሆኑም 'እንነጋገር' ማለት 'ተማረኩልኝ' ማለት ነው" ሲሉ ገልጸው፤ ገለልተኛ የአፍሪካ ሀገራት ባሉበት ድርድር መደረግ እንዳለበትም ተናግረዋል።

"ግጭቶች እያደጉና እየሰፉ የዜጎች ችግርና ሰቆቃ እየጨመረ የመጣ ሲሆን፤ መቋጫው የት ነው የሚለው የእኛም ጥያቄ ነው" ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ የአዲስ አበባ ኮሚቴ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አበበ አካሉ ናቸው።

"የመንግሥት የመጀመሪያ ኃላፊነት የሀገርና ሕዝብን ደህንነትን ማስጠበቅ ቢሆንም፤ ይኼን ማድረግ ግን አልቻለም" ሲሉ ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የገለጹት፡፡

አክለውም "በጠብመንጃ የሚመጣ ሰላም ዘላቂነቱ ጥያቄ ውስጥ የሚገባ ነው" ብለዋል።

በዚህም በሁለቱ ክልሎች የተፈጠሩ ግጭቶችን መነሻ ማጤን እንደሚገባ ያሳሰቡ ሲሆን፤ "መንግሥት በራሱ መዋቅር ውስጥ ያሉ ችግሮችን መፈተሽ ይገባዋል" ባይ ናቸው።

አክለውም፤ "የሰላም እና የጸጥታ ጉዳይ ሁሌም በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በጥያቄ መልክ የሚነሳ ቢሆንም የሚመለሰው መልስ አጥጋቢ አለመሆንና መሬት ላይ ወርዶ የተሰራ ሥራና ውጤት ግን የለም" ብለዋል።

ከአሐዱ ጋር ቆይታ ያደረጉ ፖለቲከኞች፤ መንግሥት በክልሎቹ ያለውን ችግር በማመን ለሀቀኛ ድርድር በመቀመጥ የዜጎችን ችግር ሊፈታ እንደሚገባ አጽንዖት ሰጥተውበታል።

ጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ በ6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ የሰላም ሁኔታን "ሾተላይ" ሲሉ መግለጻቸው አይዘነጋም።

በፍርቱና ወልደአብ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 12:43


የገንዘብ ሚኒስቴር የፍራንኮ ቫሉታ ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ተፈቅደው የነበሩ ምርቶች ፍቃድ መሰረዙን አስታወቀ

ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔውን ያሳለፈው መንግሥት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ተከትሎ የዋጋ ግሽበት እንዳይከሰት በሚል እንደነበር የገለጸ ሲሆን፤ አሁን ላይ ዋነኛውን ምእራፍ የታለፈ በመሆኑ ፍቃዱን አንስቻለሁ ብሏል።

ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ተፈቅደው የነበሩ የምግብና የፋብሪካ ግብአት የሚውሉ የውጭ ምርቶች መሆናቸውን አሐዱ በሚኒስትሩ አሕመድ ሽዴ ተፈርሞ የወጣ ደብዳቤ ላይ ተመልክቷል።

የፍራንኮ ቫሉታ ፍቃዱን ከጥቅምት 29/2017 ዓም ጀምሮ ተግባራዊ የማይደረግ መሆኑን ለጉምሩክ ኮሚሽን አባሪ አድርጎ በላከው ደብዳቤ ላይ ተገልጿል።

መንግሥት የተሟላ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉንና ወደ ከፍተኛ ምእራፍ እየተሸጋገረ በመሆኑን ገልጾ፤ ኢኮኖሚው መልካም ውጤቶች የታየበት መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በተመለከተ በኢትዮጵያ ያሉ ንግድ ባንኮች በቂ የሚባል የውጭ ምንዛሪ በበቂ ሁኔታ እየቀየረ ስለመሆነ ከእንግዲህ በኃላ ፍራንኮቫሉታ የሚባል ነገር እንደማይኖር የገንዘብ ሚኒስቴር በሚኒስቴሩ አሕመድ ሺዴ ተፈርሞ የወጣን ደብዳቤ ያሳወቀው።

በአማኑዔል ክንደያ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 11:57


የሸበሌ ወንዝ ሙላት በሶማሊ ክልል ሦስት ወረዳዎች የንብረት ውድመት አደረሰ

ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሸበሌ ወንዝ ሞልቶ ባስከተለው የጎርፍ አደጋ ምክንያት በሶማሊ ክልል ሸበሌ ዞን ሥር በሚገኙ ሦስት ወረዳዎች የንብረት ውድመት ማድረሱ ተገልጿል።

የጎርፍ አደጋው በሸበሌ ዞን ቀላፎ፣ ሙስታሂልና ፌርፌር ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎች ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፤ በተለይም በቀላፎ ወረዳ ባሉ ሰባት ቀበሌዎች በንብረት እና በመኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት ማድረሱን የክልሉ ሚዲያ ዘግቧል።

አደጋውን ተከትሎ በአከባቢው የሚኖሩ ዜጎች በአንስተኛ ጀልባዎች ቦታውን ለቀው እንዲወጡ የተደረገ ሲሆን በጎርፉ ከቤት ንብረታቸው የተፈናቀሉና የተጎዱ ነዋሪዎችን ለማገዝ ርብርብ እየተደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል።

የሸበሌ ወንዝ ሙላት በተደጋጋሚ በሸበሌ ዞን ጉዳት ያደረሰ ሲሆን፤ በነሐሴ ወር 2016 በተመሳሳይ ወረዳዎች በደረሰው የጎርፍ አደጋ ሁለት ሺሕ 827 አባወራዎች ከመኖሪያ ቀያቸው ሲፈናቀሉ፤ 6 ሺሕ 186 ሄክታር የሰብል መሬት ላይ ጉዳት ማድረስ ይታወሳል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 11:24


በኢንቨስትመንት ባንክ ዘርፍ የሚሰማሩ ኩባንያዎች ወደ ፋይናንስ ገበያው እንዲገቡ መንግሥት ግፊት ሊያደርግ ይገባል ተባለ

ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ የፋይናንስ ስርአት የንግድ ባንኮች ተፅእኖ የሚስተዋልበት በመሆኑ ዘርፉ ሌላ አማራጭ መመልከት ይኖርበታል ሲሉ የቢዝነስና ኢንቨስትመንት አማካሪዎች ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን "በኢንቨስትመንት ባንክ መቋቋም የሚሹ ኩባንያዎቹ በሩን ክፍት አድርጌያለሁ" ቢልም እስካሁን የተቋቋሙ የኢንቨስትመንት ባንኮች አለመኖራቸውን፤ የቢዝነስና ኢንቨስትመንት አማካሪው አቶ ያሬድ ኃይለመስቀል ለአሐዱ ተናግረዋል።

የኢንቨስትመንት ባንኮች ለፋይናንስ ስርአቱ መረጋጋትና መነቃቃት የሚሰጡት ጥቅም ከፍተኛ መሆኑን ነው አማካሪው የገለጹት።

የኢንቨስትመንት ባንኮች ለባንክ ስርአት ውጤታማነትና ቅልጥፍና የሚሰጡት ጥቅም በሌሎች አገራት ያለውን ልምድ የጠቀሱት አቶ ያሬድ፤ "በዘርፉ የሚሰማሩ ኩባንያዎች ወደ ኢትዮጵያ ፋይናንስ ገበያ እንዲገቡ መንግሥት ግፊት ሊያደርግ ይገባል" ብለዋል።

በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ያሉ ንግድ ባንኮች የሚከተሏቸው አንድ ሕጎች ለንግዱ ዘርፍ አመቺ እንዳልሆኑ የሚናገሩት ሌላኛው በዚሁ ዙርያ ያነጋገርናቸው የቢዝነስና ኢንቨስትመንት አማካሪ አቶ ከፈለኝ ኃይሉ ናቸው።

በኢትዮጵያ ያለውን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ አሁን ካለው ለውጥ በላይ መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች መኖራቸውን አማካሪዎቹ ለአሐዱ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አሁን ላይ በኢትዮጵያ ውስጥ 32 ንግድ ባንኮች፣ 1 ልማት ባንክ፣ 18 ኢንሹራንስ ኩባንያዎቹ እና 64 ማይክሮፋይናንስ ተቋማት የፋይናንስ ገበያውን እያቀለጣጠፉት ይገኛል ተብሏል።

በአማኑዔል ክንደያ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 08:49


በሦስት ወራት ውስጥ በተከሰቱ 127 አደጋዎች 93 ነጥብ 6 ሚልዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙ ተገለጸ

👉በአደጋዎቹ የ22 ሰዎች ሕይወት አልፏል


ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 ዓ.ም. ብቻ ባጋጠሙ 127 አደጋዎች 93 ነጥብ 6 ሚልዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን እና የ22 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ከደረሱት አደጋዎች 117ቱ በአዲስ አበባ ቀሪዎቹ 10 አደጋዎች ደግሞ በሸገር ከተማ ያገጠሙ ስለመሆናቸው ተነግሯል፡፡

የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ንጋቱ ማሞ ለአሐዱ በሰጡት መረጃ እንዳሉት፤ ካጋጠሙት አደጋዎች መካከል 63ቱ የእሳት ቃጠሎ፣ 28ቱ የጎርፍ፣ 18ቱ የንግድ ቤቶች ቃጠሎዎች ሲሆኑ 64ቱ ደግሞ ሌሎች ድንገተኛ አደጋዎች ናቸው፡፡

በደረሱት አደጋዎች ምክንያት የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችን ጨምሮ 12 ሰዎች ላይ ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡

የደረሱትን አደጋዎች ለመቆጣጣር በተደረገ ርብርብ በአደጋ ውስጥ የነበሩ 72 ሰዎችን እና 2 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር የሚገመት ንብረት ማትረፍ መቻሉንም የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ተናግረዋል፡፡

አሁን ያለው ደረቅና ነፋሻማ አየር ድንገተኛ የእሳት አደጋን በማባባስ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ስለሚያበረክት ሕብረተሰቡ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል፡፡

በእመቤት ሲሳይ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 08:15


ኢትዮጵያን ማጥቃት የሚፈልግ ማንኛውም አካል መጀመሪያ የሚያጠቃው ንግድ ባንክን ነው ተባለ

ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ለሳይበር ጥቃት ከትናንሽ ተቋማት ይልቅ ትልቅ ተቋማት ተጋላጭ መሆናቸውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ ተናግረዋል።

"ትልቅ ተቋማት በቀላሉ ለመጠቃት ይዳረጋሉ" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ "በዚህም ኢትዮጵያን በሳይበር ጥቃት ሊፈፅም የሚያስብ ማንኛውም አካል በቅድሚያ የሚያጠቃው የኢትዮጵያን ንግድ ባንክ ነው" ብለዋል።

"አዲስ አበባን ለማጥቃት የሚፈልግ አካል መጀመሪያ ሊያጠቃ የሚችለው የንግድ ባንክ ሕንፃን ነው፡፡ ምክንያቱም ትልቅ በመሆኑ" ሲሉም ፕሬዝዳንቱ አስረድተዋል።

"በመሆኑም ተጋላጭ መሆናችንን በመገንዘብ በቂ የሳይበር ደህንነት ሥራዎችን ከሌሎች ባለድርሻዎች ጋር በመሆን እየሰራን እንገኛለን" ብለዋል።

አክለውም "በዲጂታል ዓለም ትንሽ ስህተት ብዙ አደጋ እንደሚያደርስ ባለፈው ዓመት በሲስተም ብልሽት የተፈጠረው ነገር ማሳያ ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ ከዚህም መማር እንደሚያስፈል ተናግረዋል።

የሳይበር ጥቃት በዓለም ላይ አሳሳቢ እየሆነ መምጣቱ የተገለጸ ሲሆን፤ በተለይም የፋይናንስ ዘርፍ ደግሞ ይበልጥ ተጋላጭ መሆኑም ተነስቷል፡፡

ባሳለፍነው ዓመት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በባንኩ የሲስተም ስህተት ምክንያት 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ማጣቱን መግለፁ አይዘነጋም፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቅርብ ጊዜያት ከደረሰበት 11 ሺሕ በላይ የሳይበር ጥቃት ላይ ሙሉ ለሙሉ ማክሸፍን ፕሬዝዳንቱ ተናግረዋል።

በአቤል ደጀኔ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 06:52


472 ሺሕ 500 ኩንታል ዩሪያ የጫነች የመጀመሪያዋ መርከብ ጂቡቲ ወደብ ደርሳለች

ጥቅምት 29/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017/18 የምርት ዘመን ከውጭ ከሚገዛው 23 ሚሊየን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ፤ 472 ሺሕ 500 ኩንታል ዩሪያ የጫነች የመጀመሪያዋ ኤም ቪ አባይ ሁለት የተሰኘች የኢትዮጵያ መርከብ ጂቡቲ ወደብ መድረሷ ተገልጿል።

በቀጣይ ቀናትም ተጨማሪ ማዳበሪያ የጫኑ መርከቦች ጂቡቲ ወደብ እንደሚደርሱ እና ወደ ሀገር ውስጥ የማጓጓዝ ሥራውም በፍጥነት እንደሚጀመር የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን አስታውቋል።

ከዚህ ቀደም ለ2017/18 የምርት ዘመን ለሚውል 23 ሚሊየን ኩንታል ዩሪያ እና ዳፕ የአፈር ማዳበሪ ግዥ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር በመንግሥት መፈቀዱ ይታወሳል።

መንግሥት በአፈር ማዳበሪያ ግዥ ላይ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ የተደረገ አዲስ የግዥ መመሪያ በማውጣቱ እና ከግዥ ጋር የተያያዙ ችግሮች በመፈታታቸው ባለፈው የምርት ዘመን 21 ቢሊየን ብር ለማዳን መቻሉንም ኮርፖሬሽኑ ገልጿል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

08 Nov, 06:00


መልካም ቀን!
አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 16:00


#አሐዱ_ወቅታዊ

የኮሪደር ልማቱ እና የማህበረሰቡ ቅሬታ!

አሐዱ በልማት ተነሽነት የተፈናቀሉ፣ "የቀበሌ ቤት ኗሪ ነን" ያሉ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 በአንድ የሕዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ የሚኖሩ የበርካታ እናቶች እና ሕጻናትን ቅሬታ ተቀብሎ እንደሚከተለው አጠናክሮታል።

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
👇
https://youtu.be/5RbrC0WiTIQ?si=2O09epRr7g9Sgzx6

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 15:47


ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኞች ቁጥር መሻሻል ማሳየቱ ተነገረ

👉 በተያዘው ዓመት ከአምስት ሚልየን በላይ ሰልጣኞች መመዝገባቸው ተገልጿል


ጥቅምት 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ባለፈው ዓመት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መግቢያ ፈተናን ወስደው ውጤት ባለማምጣታቸው፤ ወደ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚገቡ ሰልጣኞች በቁጥር ደረጃ መሻሻል መታየቱን ተነግሯል።

ቴክኒክና ሙያ ስልጠና የትምህርት ተቋማት ካላቸው ዝግጁነት አንፃር የሰልጣኞች ቁጥር የመቀነስ አዝማሚያ ሲስተዋልባቸው የቆየ ቢሆንም፤ አሁን ላይ የመሻሻል ሁኔታዎች መታየታቸው ነው የተገለጸው።

በዚህም መሠረት በተያዘው በጀት ዓመት ካለፉት ዓመታት በተሻለ መልኩ አብላጫ ቁጥር ያላቸው ሰልጣኞች ተቀብለው እያስተናገዱ መሆናቸውን የፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለአሐዱ አስታውቋል።

በቅርቡ ፀድቆ ሥራ ላይ በዋለው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የትምህርት ተቋማት አዋጅ መሠረት ማሻሻያ የተደረገባቸው ጉዳዮች መኖራቸውን የገለጹት፤ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ብሩክ ከድር ናቸው።

በዚህም መሰረት የአዋጁ ማስፈጸሚያ መመርያዎች መዘጋጀታቸውን ዋና ዳይሬክተሩ ለአሐዱ ገልጸዋል።

ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘው፤ በኢትዮጵያ ያሉ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የትምህርት ተቋማት የተጣለባቸው ሐላፊነት ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው፤ የሰው ሀብት ልማትና የሙያ ብቃት ላይ በብርቱ እየተሰራበት መሆኑን ተናግረዋል።

በተያዘው በጀት ዓመትም ከአምስት ሚልየን በላይ ሰልጣኞች መመዝገባቸውን የገለጹ ሲሆን፤ ለዚህም የፌደራሉ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የአዋጁ ተፈፃሚነት በብርቱ እየተከታተለ እንደሚገኝ ዋና ዳይሬክተሩ ለአሐዱ አብራርተዋል።

የቴክኒክና ሙያ የትምህርት ተቋማት ከዚህ በቀደሙ ዓመታት ሰልጣኞችን የመቀበል አቅማቸው ከፍተኛ እንደነበር ገልጸው፤ ከዚህ ቀደም በታለመለት ልክ ሰልጣኞችን ማግኘት እየቻሉ እንዳልነበር ጠቅሰዋል።

ይሁንና ኢንስቲትዩቱ በዘርፉ ባካሄደዳቸው አንዳንድ ለውጦች ምክንያት አሁን ላይ ወደ ቀደመው ዝናው የመመለስ ጥረቶች እየተሳኩለት መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ሲናገሩ ሰምተናል።

በአማኑዔል ክንደያ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 15:18


ቴግሬቶል የተሰኘ በአፍ የሚወሰድ ፈሳሽ መድኃኒት ጨቅላ ሕጻናት እንዳይጠቀሙት ማሳሰቢያ ተሰጠ

ጥቅምት 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ቴግሬቶል የተሰኘ በአፍ የሚወሰድ ፈሳሽ (Oral Suspension) መድኃኒት ጨቅላ ሕጻናት እንዳይጠቀሙት የኢትዮጵያ ምግብ እና መድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን አሳስቧል።

ቴግሬቶል የተሰኘ በአፍ የሚወሰድ ፈሳሽ (Oral Suspension) መድኃኒት ኖቫርቲስ ፋርማ ሽዌይዝ AG/ Novartis Pharma Schweiz AG በተባለ የገበያ ፍቃድ ባለው የመድኃኒት አምራች ፋብሪካ የሚመረት ነው።

ቴግሬቶል (ካርባማዜፔይን) 100 mg/5ml Oral Suspension (OS) የተሰኘው መድኃኒት አብዛኛውን ጊዜ አጠቃላይ ለሚጥልና ከፊል መንቀጥቀጥ/ management of generalized tonic clonic and partial seizures ለማከም የሚያገለግል መሆኑንም ባለስልጣኑ ገልጿል።

ነገር ግን መድኃኒቱ በውስጡ በሚይዘው ፕሮፓይሊን ግላይኮል (propylene glycol) የሚባል ንጥረ-ነገር መጠን ምክንያት፤ ለጨቅላ ሕጻናት ማለትም ከ4 ሳምንታት በታች ለሆኑ ሕፃናት ወይም በሦስት ወራት የመወለድ ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕጻናት ሊወስዱት እንደማይመከር ማሳሰቢያ ተላልፏል

በዚህ ምርት ውስጥ ከሚገኙት ተጨማሪ ንጥረ ነገሮች አንዱ የሆነው ፕሮፓይሊን ግላይኮል ለምግብ እና ትንባሆ ምርቶች እንዲሁም ለፋርማሲዩቲካል እና መዋቢያዎች በአጠቃላይ በአሜሪካ የምግብ እና የመድኃኒት አስተዳደር (FDA) ደህንነቱ የተጠበቀ እንደሆነ ባለስልጣኑ ገልጿል።

ነገር ግን በዚህ ምርት ውስጥ ያለው መጠን በዚህ የማሳወቂያ መልዕክት ላይ ከተጠቀሱት ለጨቅላ ሕፃናት እና ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት እስከ ሦስት ወር ድረስ ከደህንነት ገደብ በላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ነው ያለው።

ስለሆነም ይህንን መድኃኒት በጨቅላ ሕፃናት ጊዜያቸው ሳይደርስ ለተወለዱ ሕፃናት እስከ ሦስት ወር ድረስ መጠቀም ጉዳቱ ከጥቅሙ የሚያመዝን በመሆኑ ሁሉም የጤና ባለሙያዎች መድኃኒቱን ለተጠቀሱት የእድሜ ክልል ከማዘዝ እና ከማከፋፈል እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

በመሆኑም ህብረተሰቡ መድኃኒቱን እንዳይጠቀም መልዕክት አስተላልፏል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 08:12


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለፈው ዓመት "በሲስተም መበላሸት" ከተወሰደበት ገንዘብ ያልተመለሰው 217 ሺሕ ብር ብቻ መሆኑን አስታወቀ

ጥቅምት 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሳይበር ድህንነት ቀንን ምክንያት በማድረግ ለመጀመሪያ ጊዜ የሳይበር ድህንነት ቀን እያከበረ ይገኛል።

በክብረ በዓሉ ላይ የተገኙት የባንኩ ፕሬዝዳንት አቤ ሳኖ፤ ባለፈው ዓመት በራሳችን ስህተት በተፈጠረው የሲስተም ችግር ምክንያት ከተወሰደው ገንዘብ ሁሉም ተመልሶ የቀረው 217 ሺሕ ብር ብቻ ነው ብለዋል።

"የሳይበር አለም አስፈሪ ነው" ያሉት ፕሬዝዳንቱ የሁሉንም ርብርብ የሚጠይቅ ሥራ ይፈልጋል ብለዋል።

"ባለፈው ዓመት የተፈጠረው ችግር በፍጥነት አጥፍፊዎች መታወቃቸው ነው እንጂ፤ ችግሩ ከውጪ የመጣና መቆጣጠር የማንችለው ቢሆን ጥፋቱ ከፍተኛ ይሆን ነበር" ብለዋል።

ባንኩ ባለፈው ዓመት መጋቢት 6 ለሊት የሲስተም ችግር በገጠመው ወቅት 2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር (40 ሚሊዮን ዶላር) እንደተወሰደበት ይታወሳል።

10 ሺሕ የሚሆኑ ግለሰቦች የገንዘብ ዝውውር ማድረጋቸውም ተገልጾ ነበር።

በአቤል ደጀኔ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 08:04


በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ባለፉት ሦስት ወራት 507 የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች አካላት መሰረቃቸው ተገለጸ

👉የሦስት ወራቱ ስርቆት በአምስት ዓመታት ውስጥ ከተፈፀመው ጋር እጅግ ተቀራራቢ ነው ተብሏል


ጥቅምት 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ባለፉት ሦስት ወራት 507 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት መሰረቃቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ አስታውቋል።

የተቋሙ እና የዞኑ አመራሮች ጋር በመሰረተ ልማት ላይ ስለሚፈፀሙ የስርቆት ወንጀሎች በተወያዩበት መድረክ ላይ የሪጅኑ የቴክኒክ ባለሙያ አቶ በሱፈቃድ ባዩ እንደገለጹት፤ በሪጅኑ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ ከ1 ሺሕ 3 መቶ በላይ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት ላይ የስርቆት ወንጀል ተፈፅሟል።

ከዚህ ውስጥ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ቦርደዴ፣ መኤሶ፣ ቡሲን አርቤ እና ኪቶን ካራ ወረዳዎች እና ቀበሌዎች 507 የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ አካላት ተሰርቀዋል።

ጉዳት የደረሰባቸውን የምሰሶ አካላት ዳግም ለመጠገን ከ2 ነጥብ 7 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን ገልጸዋል።

ከ2011 እስከ 2016 ዓ.ም መጨረሻ ድረስ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎች በሚያልፉ 119 የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ምሰሶዎች ላይ 744 ብረቶች ለስርቆት እንደተዳረጉ የጠቀሱት ባለሙያው፤ ስርቆት የተፈፀመባቸውን የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ጠግኖ ወደ ሥራ ለማስገባት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ መደረጉን አስታውሰዋል።

እንደ አቶ በሱፈቃድ ገለጻ፤ በዞኑ እና በከተማ አስተዳደሮቹ ባለፉት ሦስት ወራት ብቻ በኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ የተፈፀመው የስርቆት ወንጀል በአምስት ዓመታት ውስጥ ከተፈፀመው ዝርፊያ ጋር እጅግ ተቀራራቢ ነው።

"ይህም በምዕራብ ሀረርጌ ዞን ስር በሚገኙ ወረዳዎችና ቀበሌዎች የሚፈፀመው የስርቆት ወንጀል አሳሳቢነቱ እየጨመረ ለመምጣቱ ማሳያ ነው" ብለዋል።

በአካባቢው በተደራጀ መልኩ ስርቆት የሚፈፀም መሆኑ፣ የወሰን ማስከበር ጉዳይ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች ቁርጠኝነት ማነስ እና የሥራ ትብብርን ከጥቅም ጋር የማያያዝ እንዲሁም ህብረተሰቡ ለፀጥታ አካላት አፋጣኝ ጥቆማ አለመስጠቱ ለስርቆቱ መባባስ አስተዋጽኦ ማድረጉን ባለሙያው ማብራራታቸውን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 06:55


በየሳምንቱ በአማካይ ከ70 ሺሕ በላይ የወባ ሪፖርቶች እንደሚደርሰው የአማራ ክልል ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ

ጥቅምት 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአማራ ክልልን ከ80 በመቶ በላይ የቆዳ ስፋት በሚሸፍኑት የምዕራብ አማራ፣ ጎንደር፣ ጎጃም እንዲሁም በምስራቅ አማራ ሰሜን ወሎ አከባቢዎች ከመስከረም ወር መግቢያ ጀምሮ ከፍተኛ የሆነ የወባ ወረርሽኝ መስፋፋቱ ተገልጿል፡፡

በክልሉ በ40 ወረዳዎች በየሳምንቱ የሚደረገው የወባ ምርመራ ሪፖርት እንደሚደርሳቸው የገለጹት፤ የአማራ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር በላይ በዛብህ ናቸው፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፤ በየሳምንቱ በአማካይ ከ70 ሺሕ በላይ የወባ ሪፖርቶች ለኢንስቲትዩቱ እንደሚደርሰው ተናግረዋል፡፡

ከወባ ወረርሽኝ ጋር ተያይዞ ከፍተኛ የመድኃኒት እጥረት መኖሩን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ጉዳዩን በተደጋጋሚ ለጤና ሚኒስቴር ማቅረባቸውን ነግረውናል፡፡

የጤና ሚኒስቴር ባሳለፍነው ሳምንት በቂ የወባ በሽታ መድኃኒት ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባቱን መግለጹ አይዘነጋም።

የወባ ወረርሽኝ በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች በስፋት እየተስተዋል የሚገኝ ሲሆን፤በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማን ጨምሮ በሰባት ወረዳዎች እንዲሆም በወላይታና በሌሎች ከተሞች እና እካባቢዎች በአሳሳቢ ደረጃ እየተከሰተ መሆኑ እየተዘገበ ይገኛል፡፡

በሌላ በኩል የዓለም ጤና ድርጅት ከቀናት በፊት አዲስ ባወጣው ሪፖርት፤ በኢትዮጵያ ከታህሳስ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ጥቅምት 10 ቀን 2017 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ፤ ከ7 ነጥብ 3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወባ በሽታ መጠቃታቸውን የገለጸ ሲሆን፤ ከእነዚህም መካከል 1 ሺሕ 157 ሰዎች መሞታቸውን አስታውቋል።

በሪፖርቱ ወባ አሁንም አሳሳቢ የጤና ስጋት መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ 75 በመቶ የሚሆነው የአገሪቱ መሬት እና 69 በመቶ የሚሆነው በነዚህ አካባቢዎች የሚኖረው ሕዝብ በተለይም ሕጻናት ለከፍተኛ አደጋ ተጋላጭ መሆናቸውንም ገልጿል፡፡

በፅዮን ይልማ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 06:24


በሰብአዊ ድጋፍ እጥረት ምክንያት አረጋዊያን ለረሀብ ተዳርገዋል ተባለ

ጥቅምት 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች በተከሰተ ድርቅ እና በሰብአዊ ድጋፍ እጥረት ምክንያት አረጋዊያን ለረሃብ መጋለጣቸውን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አስታውቋል።

ኮሚሽኑ በሰጠው መግለጫ እንዳለው፤ ችግሩ በአረጋዊያን እና የአዕምሮ ሕሙማን መንከባከቢያ ማዕከላት ውስጥም መታየት ጀምሯል።

በአዕምሮ ሕሙማን መንከባከቢያ ማዕከላት ውስጥ በሚገኙ ሴት የአዕምሮ ሕሙማን ላይ ጾታዊ ጥቃት ስለመኖሩም መግለጫው አንስቷል።

በሚጣሉ የሰዓት እላፊ እና የእንቅስቃሴ ገደቦች ምክንያት በአነስተኛና ጥቃቅን የንግድ ሥራ ዘርፍ የሚተዳደሩ አካል ጉዳተኞችና አረጋውያን የችግሩ ሰለባ መሆናቸውንም አብራርቷል።

ኢሰመኮ በመግለጫው "አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የክልል ከተሞች በሚካሄዱ የልማት ሥራዎች አመቺ እና ተደራሽ ምትክ ቦታዎች ባለመሰጠታቸው አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ለከፍተኛ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሥነ-ልቦናዊ ቀውስ ተጋልጠዋል" ብሏል።

የአካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ሰብአዊ መብቶችን በተሟላ ሁኔታ ለማክበር፣ ለመጠበቅ እና ለማስፋፋት ያስችላሉ ያላቸውን ምክረ ሐሳቦችም በመግለጫው አካቷል።

በምክረ ሐሳቡም የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እስከ አሁን በረቂቅ ደረጃ የሚገኘው የአካል ጉዳተኞች መብቶች አዋጅ ግልጽና አሳታፊ በሆነ መንገድ ፍትሕ ሚኒስቴርን ጨምሮ ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ወደ ሥራ ሊገባ የሚችልበትን ሁኔታ እንዲያመቻች የጠየቀ ሲሆን፤ ሌሎች መስተካከል እና መሻሻል አለባቸው ያላቸውን ጉዳዮች አንስቷል።

በወልደሀዋሪያት ዘነበ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 06:04


ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን ወደ ሌጎስ እንደሚያደርግ ተገለጸ

ጥቅምት 28/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን ወደ ናይጀሪያ ሌጎስ እንደሚያደርግ አየር መንገዱ አስታውቋል።

ይህ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን፤ ከፈረንሳይ ቱሊስ ተነስቶ ከትናንት በስቲያ ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ መግባቱ ይታወቃል።

አውሮፕላኑ ወደ አዲስ አበባ ሲገባ አቪዬሽን ሳንስ ፍሮንቲርስ ከኤርባስ ኩባንያ ጋር በመተባበር ለኢቲ ፋውንዴሽን ያበረከቱትን ከ100 ሺሕ ዩሮ በላይ የሚያወጣ የሕክምና ቁሳቁሶች ይዞ መግባቱም ይታወሳል።

አሁን ደግሞ የመጀመሪያ በረራውን ከአዲስ አበባ ወደ ናይጀሪያ ሌጎስ እንደሚያደርግ ተነግሯል።

ይህ ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ዋሽንግተን ዲሲ፣ ለንደን፣ ፓሪስ እና ፍራንክፈርትን ጨምሮ፤ ወደ ሌሎችም ቁልፍ መዳረሻዎች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሳደግ እንደሚያስችለው ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ሰዓት የ ኤ350 ቤተሰብ የሆኑ 21 አውሮፕላኖች ባለቤት ነው።

በሚቀጥሉት ዓመታት 11 ኤ350-900 እና ሦስት ተጨማሪ ኤ350-1000 አውሮፕላኖችን ጨምሮ 14 ተጨማሪ ኤ350 አውሮፕላኖችን የአየር መንገዱ ይረከባል ተብሎ ይጠበቃል።

የኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን በአጠቃላይ 395 መንገደኞችን (46 ቢዝነስ እና 349 የኢኮኖሚ ደረጃ መቀመጫዎች) ማስተናገድ የሚችል ነው።

"ምድረ ቀደምት ኢትዮጵያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ አውሮፕላን፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድን የመንገደኞችን የማጓጓዝ አቅም ያሳድጋል ተብሎለታል።

A350 በዓለም ላይ በጣም ዘመናዊ እና ቀልጣፋ የሆነ ባለ ግዙፍ አካል አውሮፕላን ሲሆን፤ እጅግ ዘመናዊ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን እና የኤሮዳይናሚክስን ውጤቶችን አካቷል።

ከቀድሞ የአውሮፕላን ስሪቶች ጋር ሲነጻጸር በበረራ ወቅት የሚፈጥረው ድምጽ 50 በመቶ ያነሰ መሆኑም ተመላክቷል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 06:01


#ADVERTISMENT
#AhaduBank
🔊ለአሐዱ ባንክ አ.ማ. ባለአክሲዮኖች በሙሉ

የባለአክሲዮኖች 3ተኛ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ጥቅም 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሚኒሊየም አዳራሽ ይካሄዳል።

በመሆኑም የባንኩ ባለአክሲዮኖች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተጠቀሰው ቀን፣ ሰዓት እና ቦታ በጉባዔው ላይ እንዲገኙ የዳይሬክተሮች ቦርድ በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል።

አሐዱ፡ባንክ
ከብዙዎች ለብዙዎች
የአሐዱ፡ባንክ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
👉https://linktr.ee/Ahadu_Bank

AHADU RADIO FM 94.3

07 Nov, 06:00


መልካም ቀን!
አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

AHADU RADIO FM 94.3

06 Nov, 14:34


#አሐዱ_ለዛና_ቁምነገር

"ባንዲራችን መሃሙድ አህመድ" በአለምነህ ዋሴ

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ከሥር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ!
👇
https://youtu.be/uClzQ0nyzvU?si=9mrfQuNs9uYWDG2v

AHADU RADIO FM 94.3

06 Nov, 10:58


በመሬት መንቀጥቀጥ ሳቢያ የመማሪያ ክፍሎች በከፊል ከጥቅም ዉጭ ሆነዋል ተባለ

ጥቅምት 27/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአፋር ክልል በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በወረዳው በሚገኙ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ተፈጥሯ ጉዳት እንደደረሰባቸው የአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አደምበላህ ሀመዱ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በወረዳው በተደጋጋሚ እየተከሰተ በሚገኘው የመሬት መንቀጥቀጥ በስፍራው የሚገኙ ትምህርት ቤቶች በከፊል ጉዳት እንደደረሰባቸው የገለጹት ዋና አስተዳዳሪው፤ በዚህም ምክንያት ተማሪዎች ከትምህርት መማሪያ ክፍል ውጭ ትምርታቸውን እየተከታተሉ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡

"በአካባቢው እየተከሰተ የሚገኘው የመሬት መንቀጥቀጥ ከዚህ ቀደም በተሰነጠቀ ቦታ ላይ በተመሳሳይ አደጋው የሚከሰትበት ሁኔታ በመኖሩ ስጋት ፈጥሯል" ሲሉም አክለዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በወረዳው ሳቡሬ ቀበሌ ኡንጋይቱ አንደኛ ደረጃና የሁለተኛ ደረጃ ት/ት ቤት በመሬት ማንቀጥቀጡ ምክንያት የት/ቤቱ ጣሪያ፣ ግድግዳ እና ወለል በመሰነጣጠቁ በመምህራን እና ተማሪዎች ላይ ጉዳት እንዳያስከትል መምህራን ተማሪዎቹ በሜዳው ላይ ለማስተማር መገደዱን አስታውቆ ነበር።

በክልሉ እየተከሰተ ያለው ተደጋጋሚ የመሬት መንቀጥቀጥ በአንዳንድ አካባቢዎች የመሬት መሰጠንቅ፣ መኖሪያ ቤቶች ላይ ቀለል ያለ መፍረስና መሰንጠቅ እንዲሁም በእንስሳቶች ከፍተኛ ድንጋጤ እና መጠነኛ ጉዳት ማስከተሉ የተነገረ ሲሆን፣ የመሬት መንቀጥቀጡ ያስከተላቸው ተደጋጋሚ ንዝረቶች አዲስ አበባ ድረስ መሰማታቸው መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ይህም የመሬት መጥቀጥቀጥ የሬክታል ስኬል መጠን ከ4 ነጥብ 5 እስከ 4 አጥብ 9 እየጨመረ የሚገኝበት ሁኔታ እንዳለ መነገሩ የሚታወስ ነው፡፡

በእሌኒ ግዛቸው

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 17:00


#አሐዱ_ልዩ_ቃለ_ምልልስ

ተጠባቂውን የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ አስመልክቶ ከአሜሪካ አለምዓቀፍ ሚዲያ ተቋም የቢዝነስ ዴቨሎፕመንት ዳይሬክተር ጋር የተደረገ ቆይታ፡፡

Exclusive interview with Joan Mower፣ Director, Office of Business Development at United States Agency for Global Media/USAGM/

ዳይሬክተሯ ከአሐዱ ጋር ያደረጉትን ቃለ ምልልስ ለመከታተል ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/GodEen_5GmM?si=idvYY9MRnDiJa_wN

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 16:55


በሩብ ዓመቱ ከ4 መቶ በላይ አቤቱታዎች ቀርበው 24 መዝገቦች እልባት ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም ገለጸ

ጥቅምት 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 ዓ.ም ሩብ ዓመት 413 አቤቱታዎች ቀርበው 24 መዝገቦች እልባት ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም የህዝብ ግንኙነትና ኮምንኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንለይ ወርቄ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

እነዚህ የቀረቡ ቅሬታዎች ደግሞ በብዛት ከመሬት ይዞታና ከትምህርት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ የቀረቡ አቤቱታዎች መሆናቸውን ሥራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡

ከቀረቡት አጠቃላይ አቤቱታዎች መካከል 172 የሚደርሱ አቤቱታዎች ደረጃቸውን ጠብቀው የቀረቡ ሲሆን፤ ቅሬታዎቹም በምርመራ ሂደት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በአንፃሩ ደግሞ 116ቱ አቤቱታዎች ደረጃውን ጠብቀው ያልቀረቡ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

ከቀረቡ አቤቱታዎች መካከል 125 መዝገቦች ተቋሙ በተሰጠው ስልጣንና መመሪያ መሰረት ተፈጻሚ ሊያደርጋቸው የማይችሉ ወይንም ተቋሙን የማይመለከቱ አቤቱታዎች መመሆናቸውን አቶ አንለይ ወርቄ ገልጸዋል፡፡

በምርመራ ላይ ያሉ መዝገቦችን በተመለከተም ክትትል እያደረጉ መሆናቸውን በመጥቀስ፤ የምርመራ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርጉም ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በአለምነው ሹሙ

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ!

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 16:40


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር መስራች አባል ሆነ

ጥቅምት 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ማህበር መስራች አባል መሆኑን አስታውቋል።

ዩኒቨርሲቲው ሩሲያ፣ ህንድና ብራዚልን ጨምሮ ከብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመሆን በጣምራ የብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ማኅበርን በመመስረት የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ ሀገር ዩኒቨርስቲ መሆኑን ገልጿል።

አራቱ የብሪክስ ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች የመሰረቱት ማህበር በትምህርት፣ በዲፕሎማሲ፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በፈጠራ ሥራ በጋራ መስራት የሚያስችላቸው መሆኑ ተጠቁሟል።

ዩኒቨርስቲው በአዲሱ የራስ-ገዝ ስትራቴጂክ እቅድ መሰረት በአጋርነትና ዓለማቀፋዊነትን ላይ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ!

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 16:24


የመዋቅር ጥያቄ ባለመመለሱ ለግጭት መንስኤ መሆኑ ተገለጸ

ጥቅምት 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ፤ የዘይሴ ቀበሌ ማህበረሰብ ለረጅም ዓመት የቆየ የመዋቅርጥያቄ እንዳለው፤ የቀበሌው ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንግዳ እሳቱ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

የማህበረሰብን የመዋቅር ጥያቄ ለመመለስ በዞንም ይሁን በክልል ደረጃ ጥናት የተደረገ ቢሆንም፤ እስካሁን ጥያቄው ምላስ አለማግኘቱን አስተዳዳሪው ገልጸዋል፡፡ ይህም በአካባቢው ለሚታየው ግጭት መንስኤ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

ከ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በኃላ ጥያቄያችንን ይመልሳል የሚል ተስፋ ቢኖርም፤ በአካባቢው ከገዢው ብልጽግና ፓርቲ ይልቅ ኢዜማ አብላጫ ድምጽ ማግኘቱን እና መመረጡን አስታውሰዋል፡፡

"በዚህም ምክንያት 'ኢዜማን ትደግፋላችሁ' በሚል በመንግሥት በኩል የዞንም ሆነ የልዩ ወረዳ እውቅና አልተሰጠውም" ሲሉ አስተዳዳሪው ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"ጥያቄያችንን ለዞኑም ሆነ ለክልሉ መንግሥት ብናቀርብም ምላሽ ማግኘት አልቻልንም" ሲሉም ነው የተናገሩት፡፡

"የማህበረሰቡ ጥያቄ ከብልጽግናም ሆነ ከኢዜማ ጋርም የሚያገናኛው ነገር የለም" ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ በአካባቢው መንገድ፣ ትምህርት ቤቶች እና የጤና ተቋማት በመንግሥት በጀት እየተሰሩ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡

የመዋቅር ጥያቄ አለመመለሱ የእርስ በእርስ ግጭቶች መንስኤ መሆኑን የገለጹት አቶ እንግዳ ፤ "በዚህም ምክንያት የጸጥታ ሀይሎችን ጨምሮ በርካታ ዜጎች እንዲሞቱና ሌሎች ጫካ እንዲገቡ ሆናል" ብለዋል፡፡

"በክልልም ሆነ በፌደራል መንግሥት መቀመጫ የያዙት የአካባቢው የህዝብ ተወካይዎች በአግባቡ ኃላፊነታቸውን አልተወጡም፡፡ የማህበረሰቡን ጥያቄ ከማንሳት ይልቅ የራሳቸውን ጥቅም ያስቀደሙ ሆነዋል" ሲሉም ወቅሰዋል፡፡

መንግሥት ይሄን የመዋቅር ጥያቄ ምላሽ ይሰጣል የሚል እምነት እና ተስፋ እንዳላቸውም አስተዳዳሪው ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በፍቅርተ ቢተው

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ!

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 15:32


#አሐዱ_አሳሩ_በዛብህ

አሳሩ በዛብህ በሳምንቱ አሳሰበኝ ያለውን ጉዳይ በብዕሩ ከትቦ ለወዳጁ ምክረ ሰናይ ልኮለታል፡፡ አሳሩን ያሳሰበው ጉዳይ ምን ይሆን?

ሙሉ ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/ARjlN73uLsA?si=AUdsPoypyoNGLQaZ

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 15:17


በዛሬው ዕለት በሸገር ከተማ ፉሪ ክፍለ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ አንድ እናት ከስድስት ወር ልጇ ጋር ሕይወቷ ማለፉ ተሰማ

👉በእሳት አደጋዉ ስድስት የንግድ ሱቆች ተቃጥለዋል ተብሏል

ጥቅምት 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በሸገር ከተማ ፉሪ ክፍለ ከተማ ዛሬ ጥቅምት 26 ቀን 2017 በመስሪያና መሸጫ ሼድ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ አንድ እናት ከስድስት ወር ልጇ ጋር ሕይወቷ ማለፉ ተሰምቷል፡፡

ከንግድ ሱቆቹ መካከል በአንደኛዉ ነዳጅ በፕላስቲክ ጠርሙስ በችርቻሮ የሚሸጥበት ሱቅ በመሆኑ ለሽያጭ የተዘጋጀዉ ነዳጅ ለቃጠሎው መከሰትና መባባስ ምክንያት ሆኗል ተብሏል።

ከስድስት ወር ልጇ ጋር ሕይወቷ ያለፈችዉ እናት በእሳት አደጋዉ ከተቃጠሉት የንግድ ሱቆች ዉስጥ በአንደኛዉ ሱቅ የንግድ ሥራ ላይ የነበረች መሆኑ ታውቋል።

በተጨማሪም በእሳት አደጋዉ በሼድ ዉስጥ ካሉ ሱቆች መካከል ስድስት የንግድ ሱቆች መቃጠላቸው ተገልጿል።

የእሳት አደጋዉን ለመቆጣጠር ሦስት የአደጋ መቆጣጠር ተሽከርካሪ፣ ሁለት አምቡላንሶች ከሰላሳ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ጋር የተሰማሩ ሲሆን፤ የእሳት አደጋዉ ወደሌሎች ንግድ ሱቆች ተዛምቶ ተጨማሪ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር መቻሉን የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ለሸገር ሬዲዮ ገልጿል።

ኮሚሽኑ ነዳጅ መከማቸትም ሆነ መሸጥ ያለበት በተፈቀደለትና የአደጋ ደህንነት መስፈርትን ባሟሉ የነዳጅ መሸጫ ጣቢያዎች ዉስጥ ብቻ መሆኑን የገለጸ ሲሆን፤ በተለያዩ የንግድ ሱቆች ዉስጥ ነዳጅ ማከማቸትም ሆነ መሸጥ መሰል አደጋዎችን የሚያስከትል በመሆኑ የንግድ ፈቃድ የሚሰጡ አካላትም ተገቢዉን ቁጥጥር ማድረግ እንደሚኖርባቸው አሳስቧል፡፡

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ!

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 14:57


#UPDATE
በአፍሪካ በአይነቱ የመጀመሪያው የሆነው ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን ዛሬ አዲስ አበባ ገባ


ጥቅምት 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአፍሪካ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውና A 350-1000 "Ethiopia land of origins" የሚል ስያሜ የተሰጠው የመንገደኞች አውሮፕላን በዛሬው ዕለት አዲስ አበባ ገብቷል።

አውሮፕላኑ አቪዬሽን ሳንስ ፍሮንቲርስ ከኤርባስ ኩባንያ ጋር በመተባበር ለኢቲ ፋውንዴሽን ያበረከቱትን ከ100,000 ዩሮ በላይ የሚያወጣ የሕክምና ቁሳቁሶች ያጓጓዘ መሆኑን የአየር መንገዱ መረጃ ያመለክታል፡፡

አዲስ አበባ ቦሌ አለም ዓቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስም ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ሀላፊዎች፣ አምባሳደሮች፣ ሚኒስተሮች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ደማቅ የአቀባበል ሥነ-ስርዓት ተደርጎለታል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን በፈረንሳይ ቱሉዝ በተካሄደ ሥነ-ስርዓት ከኤርባስ ኩባንያ መረከቡ ይታወቃል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 14:27


በሕገ-ወጥ እርድ የተከናወነ ከ2 ሺሕ 8 መቶ ኪሎ ግራም በላይ ሥጋ መወገዱ ተገለጸ

ጥቅምት 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በሕገ-ወጥ እርድ የተከናወነ ከ2 ሺሕ 8 መቶ ኪሎ ግራም በላይ የሚመዝን ሥጋ ማስወገዱን የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አስታውቋል፡፡

በሦስት ወራት ውስጥ ከ1 መቶ 8 ሺሕ በላይ የእንስሳት እርድ ለማከናወን በእቅድ ተይዞ እንደነበር የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አታክልቲ ገብረ ሚካኤል ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"ከእቅዱ ውስጥም ከ1 መቶ 2 ሺሕ በላይ በሚሆኑ እንስሳት ላይ ደህንነቱ የተጠበቀ እርድ ተከናውኗል" ብለዋል፡፡

ኃላፊው ከአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ከአዲስ አበባ አርሶአደር እና ከተማ ግብርና ኮሚሽን እንዲሁም ከሌሎች ጋር በመሆን በሕገ-ወጥ እርድ ላይ የክትትል ሥራዎችን እንደሚያከናውኑ ተናግረዋል፡፡

በክትትላቸውም የሚያጋጥሙ ሕገ-ወጥ እርዶችን የሚያስወግዱት አሰራር ስለመኖሩ ገልጸው፤ በሦስት ወራት ውስጥ ከ2 ሺሕ 8 መቶ ኪሎግራም በላይ የሚመዝን በሕገ-ወጥ መንገድ የተከናወነ እርድ መወገዱን ጠቁመዋል፡፡

የሩብ ዓመቱ የበዓላት ወቅት እንደነበር የተናገሩት ኃላፊው፤ የሚከናወነው የእንስሳት እርድ የሚጨምርበት ሁኔታ ስለመኖሩ ተናግረዋል፡፡

ለህብረተሰቡ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የተመረመረ የእርድ አገልግሎት እንደሚሰጡ የገለጹ ሲሆን፤ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የጨመረበት ሁኔታ መኖሩንም አመላክተዋል፡፡

በእሌኒ ግዛቸው

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ!

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 13:02


#አሐዱ_ትንታኔ

በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ አለዛም የዲሞክራቱዋ ካማላ ሀሪስ ኋይት ሀውስ ቢገቡ፤ አሜሪካ ብሎም የተቀረው አለም ምን አይነት ለውጦችን ሊያስተናግድ ይችላል የሚለው የዛሬ አለማቀፍ ትንታኔ ትኩረታችን ነው፡፡

ሙሉ ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/DsqfHCyTqh8?si=ugNHIkKIuyciNtA7

AHADU RADIO FM 94.3

05 Nov, 12:43


የክቡር ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ አልባሳትና ቁሳቁስ ለዕይታ ሊቀርብ ነው

ጥቅምት 26/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ አልባሳት እና ቁሳቁስ ትውልድ እንዲያየው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጥናትና ምርምር ተቋም ጥቅምት 29 ቀን 2017 በክብር ይቀመጣል ተባለ፡፡

በዕለቱም የአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ አድናቂዎች እና ሌሎች እንግዶች እንደሚገኙ የክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ የመታሰቢያ ዝግጅት አስተባባሪ ኮሚቴ ለኤፍ ቢ ሲ አስታውቋል፡፡

ታሪካዊ የሆኑ እና በትውልድ ቅብብሎሽ ውስጥ ኅያው ሆነው እንዲኖሩ ከአርቲስቱ ቤተሰቦች የተሰበሰቡ አልባሳት እና ቁሳቁሶችንም አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተረክቦ ለዕይታ እንዲበቃ በባለቤትነት ይረከባል ተብሏል፡፡

አርቲስቱን የሚያስታውስ የፎቶ ዐውደ-ርዕይ እና ሥራዎች በዕለቱ ለታዳሚያን እንደሚቀርቡም ተጠቁሟል፡፡

ክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ከ400 በላይ የሙዚቃ ሥራዎችን ያበረከተ ሲሆን፤ ወደ 40 ከሚጠጉ የግጥምና ዜማ ደራሲዎች በወሰዳቸው የሙዚቃ ሥራዎቹ ስለፍቅር፣ ስለአገር፣ ስለቤተሰብ፣ ስለፖለቲካ፣ ስለተፈጥሮ ስለማኅበራዊ ጉዳዮች የተጫወተ ታላቅ የሙዚቃ ባለሙያ እንደነበር አይዘነጋም።

ክቡር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ ሚያዚያ 11 ቀን 2001 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፉ ይታወቃል።

#አሐዱ_የኢትዮጵያውያን_ድምጽ!

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 14:44


ጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ ራሱን የቻለ ገለልተኛ ተቋም ሆኖ ሊቋቋም ይገባል ተባለ

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ ያለውን የፍትህ ስርአት ሚዛናዊና ተቋማዊ እንዲሆን ካስፈለገ ጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ ከፍትሕ ሚኒስቴር ተነጥሎ ራሱን መቻል አለበት ሲሉ የሕግ ባለሙያዎች ተናግረዋል።

ባለሙያዎቹ ጠቅላይ "ዐቃቢ ሕግ ራሱን የቻለ ተቋም ሆኖ መቋቋም ባለመቻሉ የፍትሕ ስርዓቱ እንዳይፀናና ተአማኒ ተቋም እንዳይሆን እያረገው ይገኛል" ሲሉም ለአሐዱ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በዘርፉ ባለሙያዎች ዘንድ ጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ ራሱን የቻለ ተቋም ሆኖ እንዲቋቋምና ከፓለቲካ ወገንተኝነት ነፃ በሆኑ ባለሙያዎች እንዲመራ ውትወታ ሲደረግ መቆየቱን ለአሐዱ ያስታወሱት፤ የሕግ ባለሙያው አቶ ታምራት ኪዳነማርያም ናቸው፡፡

ጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ ራሱን ችሎ መቆም ባለመቻሉና የፍትሕ ሚኒስቴር ጥገኛ እንዲሆን በመደረጉ ምክንያትም የፍትህ ስርአቱና የሕግ የበላይነት እንዲሸረሸር አድርጎታል ባይ ናቸው።

'የፍትህ ስርአቱ ገለልተኛ ነው' ማለት የሚቻለው፤ ጠቅላይ ዐቃቢ ሕግ ከፍትሕ ሚኒስቴር ተነጥሎ መውጣት ሲችልና ራሱን በራሱ ሲመራ ብቻ መሆኑንም አቶ ታምራት ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ እየተስተዋለ ያለው የፍትህ ስርአቱ መዛባት፤ የገለልተኝነት ጥያቄ ባለመፈታቱ ምክንያት የመጣ መሆኑንም አንስተዋል።

ሌላኛው በዚሁ ዙርያ ሐሳባቸውን እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የሕግ ባለሙያ ደበበ ወልደገብርኤል በበኩላቸው፤ "በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት እንዳይኖር ካደረጉ ምክንያቶች ውስጥ አንዱ የፍትሕ ስርአቱ ከፓለቲካ ጣልቃ ገብነትና ጫና መላቀቅ አለመቻሉ ነው" ብለዋል፡፡

ባለሙያው አክለውም፤ የፍትሕ ሚኒስቴር የፓለቲካ ተቋም እንደመሆኑ መጠን በፍትሕ ስርአቱ ላይ ገለልተኛ ነው ብሎ መውሰድ እንደማይቻል ነግረውናል።

"የፍትህ ሚኒስቴር በአገሪቱ ለፍትሕ መዛባትና በሕግ ላይ ተአማኒነት ማጣት ምክንያትም፤ ከሚኒስቴሩ እጅ ወጥተው በገለልተኛ ተቋም መተዳደር የነበረባቸው ጉዳዮች በመኖራቸው ነው" ሲሉም አክለዋል፡፡

"በአገር ውስጥ ያለውን የፍትህ ስርአት የተስተካከለ እንዲሆን ከተፈለገ፤ የሚመለከታቸው አካላት ጉዳዩን በሚገባ ማጤን ይኖርባቸዋል" ሲሉም ባለሙያዎቹ ለአሐዱ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በአማኑዔል ክንደያ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 14:19


የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በነገው ዕለት 4ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሂዳል

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ስብሰባ በነገው ዕለት ይካሄዳል፡፡

ምክር ቤቱ ነገ በሚያካሂደው መደበኛ ስብሰባ የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችን መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡

በሌላ በኩል የፌዴራል የፍትህና የህግ ኢንስቲትዩትን እንደገና ለማቋቋም የቀረበ ረቂቅ አዋጅን መርምሮ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መምራት ምክር ቤቱ በነገው መደበኛ ስብሰባ የሚወያይበት ሌላኛው አጀንዳ መሆኑን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 12:44


የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ምደባ ይፋ ተደረገ

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የREMEDIAL ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ምደባቸውን ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

ስለዚህም ተማሪዎች፡-
Website: https://placement.ethernet.edu.et
Telegram: https://t.me/moestudentbot ላይ ምደባውን መመልከት ይችላሉ ተብሏል፡፡

ተማሪዎች ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራሙን እንዲከታተሉ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 12:32


#UPDATE
ተቋርጦ የነበረው የድሬዳዋ ሀረር እና ሱማሌ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሥራ ጀመረ

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ጥቅምት 23 ቀን 2017 በእሳት አደጋ ምክንያት በጊዜያዊነት አገልግሎት መስጠት ያቋረጠውን የድሬዳዋ ቁጥር 3 ማከፋፈያ ጣቢያ መስመር የማዛወር ሥራ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታውቋል፡፡

በዘርፉ የምስራቅ አንድ ሪጅን የኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ፤ ትናንት ምሽት ከ1:00 ሰዓት እስከ ሌሊት 11፡00 ከሁርሶ ወደ ድሬዳዋ አንድ፣ ወደ ሀረር እና ጅግጅጋ የሚሄዱ መስመሮችን የማዛወር ሥራ መሰራቱን ገልጸዋል፡

በዚህም መሰረት ዛሬ ረፋድ መስመሩን የመፈተሽ ሥራ ተከናውኖ ወደሁሉም አካባቢዎች ኃይል እንደደረሰ መረጋገጡን ተናግረዋል።

የሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ጉዳት እንዳጋጠመው ተደርጎ የተሰራጨው ዘገባ የሀሰት መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ፤ ከሁርሶ ማከፋፈያ ጣቢያ ተጨማሪ ወጪ መስመር በማዘጋጀት ችግሩ መፈታቱን አስታውቀዋል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 11:54


የደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ የሚገኙ መምህራን ከ2 ወር በላይ ደምወዞ ስላልተከፈላቸው ለተለያየ ችግር እየተጋለጡ መሆኑን ገለጹ

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ወግዲ ወረዳ የመምህራን ደምወዝ ከ2 ወር በላይ ባለመከፈሉ ምክንያት፤ ለተለያዩ ችግሮች እየተጋለጡ መሆኑን የአካባቢው መምህራን ለአሐዱ ቅሬታቸዉን አሰምተዋል።

በአካባቢው ባለው የጸጥታዉ ችግር ምክንያት የተዘጉ  ትምህርት ቤቶች መኖራቸውን የገለጹት መምህራኑ፤  ከመስከረም ወር 2017 ጀምሮ ደምወዝ እየተከፈላቸዉ እንዳልሆነ ተናግረዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ የሚተዳደሩት በማስተማር በሚያገኙት የወር ደሞዛቸዉ ብቻ በመሆኑ ደምወዛቸዉ ሲቋረጥ ልጆጃቸዉን ለማስተዳደና የዕለት ጉርስ ለማግኘት መቸገራቸውን የገለጹ ሲሆን፤ የመምህራንን ደሞዝ ማቋረጡ ተገቢ እንዳልሆነ ተናግረዋል።

በአካባቢዉ የተዘጉ ትምህርት ቤቶችን እንዲከፈቱና የመምህራን ደምወዝ እንዲከፈላቸዉም ለሚመለከታቸው አካላት ተደጋጋሚ ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ አለማግኘታቸውን ጨምረው ገልጸዋል።

አክለዉም የደሞዝ ክፍያን በተመለከተ የሚመለከተዉን አካል ሲይቁ፤ "ትምህርት ቤቶች ስለተዘጉ እናንተም ሳታስተምሩ ደሞዝ አይከፈላችሁም" የሚል ምላሽ እንደሰጧቸዉ ተናግረዋል።

ደሞዝ ያልተከፈላቸዉ መምህራን እንደ አጠቃላይ በግምት ከ700 በላይ እንደሚሆኑም ለአሐዱ ገልጸዋል።

አሐዱም ይህንን ችግር በተመለከተ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮን ለማነጋገር ያደረገዉ ጥረት አልተሳካም። ምላሹን እንዳገኘን ወደእናንተ የምናደርስ ይሆናል።

በአለምነው ሹሙ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 10:26


#አሐዱ_ትንታኔ

በመላው አሜሪካ እየተጠበቀ ያለው ደግሞም የአሜሪካን ግዙፍ ፓርቲዎች ማለትም ሪፐብሊካንን እና ዲሞክራትን ፊት ለፊት የሚያፋጥጠው ምርጫ በነገው ዕለት ይካሄዳል፡፡

የፕላኔቷ ልዕለ ሃያል ሀገር አሜሪካን ቀጣይ አራት ዓመታት እጣ ፈንታ ለመወሰን ሥልጣነ መንበሩን ከተሰናባቹ ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ማን ይረከባል? የሚለው ጥያቄ፤ በነገው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ምላሽ ያገኛል፡፡

ይህን የአሜሪካን ቀጣይ ዕጣ ፈንታ ብቻ ሳይሆን የሌሎችንም ሀገራት ዕጣ ፈንታ የመበየን አቅም ያለውን ፕሬዝደንታዊ ምርጫ እና የእስከአሁን የቅድመ ምርጫ ቀን ድምጽ ውጤት እና ተያያዥ ጉዳዮችን በዛሬው የአለም አቀፍ ትንታኔያችን ተመልክተነዋል፡፡

ሙሉ ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/yQJyOB4j57Q?si=5yw9CFtntv1i1U2E

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 10:06


በኢትዮጵያ 22 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች በሚደርስባቸው መገለል ምክንያት ከትምህርታቸው ወደኋላ እንደሚቀሩ ተገለጸ

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ 22 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች በሚደርስባቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ መገለሎች ምክንያት ከትምህርታቸው ወደኋላ እንደሚቀሩ የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት አስታውቋል፡፡

የሴቶች ማህበራት ቅንጅቱ በአማራ፣ ኦሮሚያ እንዲሁም ትግራይን ጨምሮ በሌሎች አምስት ክልልሎች የሴቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና እና ተሳትፎን በሚመለከት የተጠናዉን ጥናት ይፋ አድርጓል፡፡

ጥናቱ በስምንት ክልሎች ለ26 ወራት የተደረገ ሲሆን፤ በሁሉም ክልሎች በአጠቃላይ ከ36 ሺሕ በላይ ሴቶች ተሳታፊ መሆናቸው ተነግሯል፡፡

በጥናቱ አሁናዊ የፖለቲካ እና ማህበራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ ተሳትፎ እና ጫናዎችን በሚመለከት ሰፊ ዳሰሳ ተደርጓል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያ 22 በመቶ የሚሆኑ ሴቶች በሚደርስባቸው የተለያዩ መገለሎች ምክንያት ከትምህርታቸው ወደኋላ እንደሚቀሩ መረጋገጡ ተገልጿል፡፡

የጥናቱ ግኝቶች የሴቶችን በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መስኮች ያላቸውን ተሳትፎ በተመለከተ ያለውን የመረጃ ክፍተት ለመሙላት ፋይዳ እንዳለው የተመላከተ ሲሆን፤ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይህንን ክፍተት ለመሙላት የበኩላቸውን እንዲወጡም ጥሪ ቀርቧል።

ከዚህ ጋር ተያይዞም ይህ ተግባራዊ ጥናት መደረጉ በሴቶች ጉዳይ ላይ የሚታዩ የፖሊሲ ክፍተቶችን ለማስተካከል እና አሳሳቢ ጉዳዮች ላይ ትኩረት እንዲደረግ ጥሩ አጋጣሚ ነዉ ተብሏል፡፡

ጥናቱን ላለፉት 2 ዓመታት የሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ሴቶች ማህበራት ቅንጅት፣ ኦክስፋም ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ልዑካን በጋራ ማከናወናቸው ተገልጿል።

በፅዮን ይልማ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: www.facebook.com/ahaduradio
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 09:10


ሶማሊያ የኢትዮጵያን ኤምባሲ ከፕሬዝዳንቱ ቅጥር ግቢ ልታስወጣ መሆኑን ገለጸች

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አህመድ ሞአሊም ፊቂ በአሁኑ ወቅት በፕሬዝዳንቱ ቤተ መንግሥት ውስጥ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ወደ ሌላ ባዶ ቦታ ለማዘዋወር መታቀዱን አስታውቀዋል።

ሚኒስትሩ ትናንት ጥቅምት 24 ቀን 2017 ዓ.ም ለሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ "ውሳኔው የተወሰነው በፕሬዝዳንቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ የውጭ ሀገር ኤምባሲ መገኘቱ፤ ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቃውሞ ማስነሳቱን ተከትሎ ነው" ብለዋል።

"የሶማሊያ ሕዝብ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሚገኝበት ቦታ ላይ ያቀረቡት ቅሬታ ተገቢ ነው።" ያሉት ሚኒስትሩ፤ "በቅርብ ጊዜ ውስጥ ከፕሬዝዳንቱ ቤተ መንግሥት ውጭ ወደሚገኝ አዲስ ቦታ እንዲዛወር ለማድረግ ፈጣን እርምጃ እንወስዳለን" ሲሉ ተናግረዋል። 

አክለውም "ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ይገኝበት የነበረው አከባቢ በአሁኑ ሰአት ምንም አይነት ጥቅም እየሰጠ አይደለም፤ እሱን አድሰን ኤምባሲው ወደዚያው እንዲዛወር እናደርጋለን" ብለዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህ ካልሆነ ግን በተመሳሳይ "በአዲሰ አበባ የሚገኘውን የሶማሊያ ኤምባሲ በኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት ግቢ ውስጥ እንዲሆን የሚል ጥያቄ እናቀርባለን" በማለት ተናግረዋል።

ይህ እርምጃ በፕሬዝዳንት አብዱላሂ ዩሱፍ አህመድ መንግሥት ፍቃድ ተሰጥቶታልም ተብሏል።

ይህ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ መግለጫ ኢትዮጵያ ከሶማሌላንድ ጋር የመግባቢያ ስምምነትን መፈራረሟን ተከትሎ፤ በኢትዮጵያ እና ሶማሊያ መካከል እየተካረረ የመጣውን ልዩነት የሚያንጸባርቅ መሆኑ ተዘግቧል።

ከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ ኢምባሲ ውስጥ በአማካሪነት የሚሰሩት አሊ መሀመድ አደም "ከዲፕሎማሲ ሥራዎች የሚጣረስ ተግባር ውስጥ ተሰማርተው ተገኝተዋል" በሚል፤ በ72 ሰዓት ውስጥ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ በሚኒስቴሩ መታዛቸውን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: www.facebook.com/ahaduradio
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 08:00


በመዲናዋ በሩብ ዓመቱ ከ42 ሚሊየን ብር በላይ ከደንብ መተላለፍ ቅጣት መገኘቱ ተገለጸ

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በተያዘው በጀት ዓመት የሩብ ዓመት አፈጻጸም ከኮሪደር ልማት እንዲሁም ከሌሎች ደንብ መተላለፎች፤ ከ42 ሚሊየን ብር በላይ መቅጣቱን የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን አስታውቋል።

ባለስልጣኑ በ2017 በጀት ዓመት 1ኛ ሩብ ዓመት የተከናወኑ የቅድመ መከላከል ሥራዎች እና የተወሰዱ እርምጃዎችን በተመለከተ ባካሄደው መድረክ ላይ ነው ይህንን የገለጸው።

በ2016 በጀት ዓመት በአጠቃላይ በዓመቱ ከደንብ መተላለፍ 66 ሚሊየን ብር መገኘቱን የገለጸው ባለስልጣኑ፤ በዚህ ሩብ ዓመት ግን ከ42 ሚሊየን ብር በቅጣት መሰብሰቡን ገልጿል።

ለዚህም በተያዘው ዓመት የቁጥጥር መጥበቁ ማሳያ መሆኑን አንስቶ፤ ከቅጣት የተሰበሰበውን ገንዘብ ለከተማ አስተዳደሩ ገቢ ተደርጓል ብሏል።

በተመሳሳይ በሩብ ዓመቱ ሕገ-ወጥ የጎዳና ንግድ፣ ሕገወጥ ግንባታዎች፣ የመሬት ወረራን ጨምሮ የተያዩ የደንብ መተላለፎች እንደነበሩ ተገልጿል።

በፍርቱና ወልደአብ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 07:39


ሱዳን የተባበሩት ዓረብ ኢምሬቶች ቀይ ባሕር ላይ አዲስ ወደብ እንድትገነባ የተደረሰውን የ6 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት መሰረዟን አስታወቀች

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሱዳን ቀይ ባህር ላይ አዲስ ወደብ እንድትገነባ ከተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ጋር የገባቸውን የ6 ቢሊዮን ዶላር ስምምነት መሰረዟን የሀገሪቱ ገንዘብ ሚኒስትር ጂብሪል ኢብራሂም ገልጸዋል፡፡

ሚኒስትሩ እሁድ ዕለት በሰጡት መግለጫ፤ "አቡ ዳቢ በሀገሪቱ እየተከሰተ ባለው ግጭት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦርን ትደግፋለች" ሲሉ ከሰዋል።

እ.ኤ.አ በታህሳስ 2022 የተፈረመው ስምምነት አቡዳቢ ከፖርት ሱዳን በስተሰሜን 200 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘውን የአቡ አማማ ወደብን በ6 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ለመገንባት እና ለማስተዳደር የሚፈቅድ ነበር፡፡

ሚኒስትሩ በመግለጫቸው፤ እ.ኤ.አ "ከታህሳስ 15 ጀምሮ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ ከሱዳን ጦር ጋር እየተዋጋ ላለው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር ድጋፍ ሰጥታለች" ያሉ ሲሆን፤ "ይህ ከሆነ በኋላ ለተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በቀይ ባህር ዳርቻ ላይ አንድ ሴንቲሜትር አንሰጥም" ብለዋል።

የተሰረዘው ፕሮጀክት ወደቡ በሚገነባበት አካባቢ ነጻ የንግድ ቀጠና ማቋቋም፣ የግብርና ፕሮጀክት እና ለሱዳን ማዕከላዊ ባንክ የ300 ሚሊዮን ዶላር ተቀማጭ ገንዘብ ያካተተ ፕሮጀክት እንደነበር የሱዳን ትሪቡን ዘገባ አመላክቷል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 07:34


#ADVERTISMENT
#ጊፍትሪልስቴት
ታላቅ የምስራች!
**************
ጊፍት ሪል ስቴት ከ10% ቅድመ ክፍያ ጀምሮ በ22 ሳይቶቹ ቅንጡ አፓርትመንቶችን እና የንግድ ሱቆችን ለሽያጭ አቅርቧል፡፡

ይህ ሳይት ለአፓርትመንትና ንግድ ሱቆች የሚውሉ G+25 ሶስት መንታ ህንጻዎች ያሉት ሲሆን የዚህ 6ኛ መንደር መለያዎች፡-
•ከባለአንድ እስከ ባለአራት መኝታ ክፍሎች ያሉት፣
•ለመኖሪያም ሆነ ለንግድ ተመራጭ አካባቢ የሆነ፣
•በአንድ ወለል ሶስት ቤቶች ብቻ ያሉት፣
•በእያንዳንዱ ወለል ስድስት አሳንስር ያለው፣
•አራት ቤዝመንት ያሉት በቂ የመኪና ማቆሚያ የተዘጋጀለት፣
•24 ሰዓት የኤሌክትሪክ፣ ኢንተርኔትና ውሃ አቅርቦት አሉት፣

ጊፍት ሪል ስቴት
ማህበረሰብን እንገነባለን!
ለበለጠ መረጃ፡-
Website: https://www.giftbusinessgroup.com
Twitter: https://twitter.com/GIFTBusinessG
YouTube: www.youtube.com/channel/UCcqr7cpVv9ski-F7haxXx4w
Facebook: www.facebook.com/profile.php?id=100090918391017...
Telegram: https://t.me/giftbusinessgroup
Short Code: 8055

AHADU RADIO FM 94.3

04 Nov, 06:41


በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን በነገው ዕለት አዲስ አበባ ይገባል

ጥቅምት 25/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው ኤርባስ ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላን፤ በነገው ዕለት አዲስ አበባ እንደሚገባ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል፡፡

አየር መንገዱ ኤ350-1000 "Ethiopia land of origins" የተሰኘ የመንገደኞች አውሮፕላን ከኤር ባስ ኩባንያ በቅርቡ እንደሚረከብ መግለጹ ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቅርቡ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በሰጡት ማብራሪያም፤ አየር መንገዱ 124 አውሮፕላኖችን ለመግዛት ማዘዙን ተናግረዋል።

በተጨማሪም አየር መንገዱ በዓመት እስከ 130 ሚሊየን መንገደኞችን ማስተናገድ የሚችል ግዙፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩን በማብራሪያቸው መግለጻቸው ይታወሳል።

ይህንንም ተከትሎ በትናንትናው ዕለት በኢፌዲሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የተመራ ልዑክ ኤር ባስ ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላንን ለመረከብ ፈረንሳይ ገብቷል፡፡

ልዑካን ቡድኑ ሌ/ጄ ይልማ መርዳሳ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው እና ሌሎች የአየር መንገዱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች የያዘ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት በነገው ዕለት አዲስ አበባ የሚገባው ኤ350-1000 አውሮፕላን፤ "በአፍሪካ አቪዬሽን ኢንደስትሪ ታሪክ የቀዳሚነታችን ማሳያ ከሆኑት ስኬቶች አንዱ ይሆናል" ሲል አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡

ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላ ለደንበኞች የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ቴክኖሎጂ የተገጠመለት ሲሆን፤ 46 የቢዝነስ ደረጃ እና 349 የኢኮኖሚ ደረጃ መቀመጫዎች በአጠቃላይ 395 መቀመጫዎች አሉት፡፡

ከሌሎች አውሮፕላኖች ጋር ሲወዳደርም ከፍተኛ የቢዝነስ ደረጃ መቀመጫዎችን ያሉት መሆኑ ተመላክቷል።

በዚህም መሰረት ኤ350-1000 የመጀመሪያ በረራውን ከአዲስ አበባ ወደ ሄትሮው ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሕዳር 3 ቀን 2024 በማድረግ ሥራ ይጀምራል ተብሎ እንደሚመጠበቅ መገለጹን አሐዱ መዘገቡ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር በ2035 በዓመት 67 ሚሊዮን መንገደኞችን በማጓጓዝ 25 ቢሊዮን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ለማግኘት እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቀ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅትም ባሉት 147 አውሮፕላኖች 139 ዓለም አቀፍና 22 የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎችን እየሸፈነ ይገኛል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 17:30


#አሐዱ_አብይ_ጉዳይ!

ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/X8v6bnMp3bQ?si=XVn_NBb9ljCWpTyV

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 14:02


በጋምቤላ ክልል የተከስተው ከፍተኛ የወባ ወረርሽኝ የመቀነስ አዝማሚያ ማሳየቱ ተገለጸ

ጥቅምት 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከዚህ በፊት በጋምቤላ ከተማ በመንገሺ እና ጎሬ ወረዳዎች ከፍተኛ የሆነ የወባ ወረርሽኝ መከሰቱን የክልሉ ጤና ቢሮ አስታዉቆ እንደነበር አይዘነጋም።

ከሰሞኑ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍልች በተለይም በአማራ ትግራይ እና በአንድ አንድ የደቡብ ኢትዮጵያ ክፍሎች ከፍተኛ የሆነ የወባ ወረርሽኝ ተከስቶ እንደነበር መገለጹ ይታወሳል።

ከዚህ ጋር ተያይዞም በጋምቤላ በሚገኙ መንገሺ እና ጎደሬ ወረዳዎች እንዲሁም በከተማው ተከሰቶ የነበረዉ ከፍተኛ የሆነ የወባ ወረርሽኝ አሁን ላይ መቀነስ ታይቶበታል ተብሏል፡፡

ለዚህ ደግሞ እንደሀገር የወባ በሽታን ለመከላከል በተጀመረው ዘመቻ የአጎበር ስርጭት እና የኬሚካል ርጭት አስተዋፅኦ ማድረጉን የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር አቤል አሰፋ ገልጸዋል።

በተጨማሪም የወባ ተጋላጭ በሆኑ የክልሉ ወረዳዎች የአካባቢ ጽዳትና ቁጥጥር ሥራዎችን በመስራት፤ የቅድመ መከላከልና ጥንቃቄ ሥራ መከናወኑን አስረድተዋል፡፡

ኃላፊዉ አክለውም የወባ ወረርሽኙን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት የማህበረሰቡን ተሳትፍ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ገልጸዉ፤ "በሌሎች ወረዳዎችና አካባቢዎችም እንዳይስፋፋ ጥረት እየተደረገ ነዉ" ብለዋል።

በፅዮን ይልማ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 12:37


የሀገርን እድገት ከፖለቲካዊ እይታ ነጥሎ ማየት ያስፈልጋል ሲሉ የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች ገለጹ

ጥቅምት 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 8 ነጥብ 1 በመቶ እድገት አስመዝግባለች፡፡ በሚቀጥለው ዓመት 8 ነጥብ 4 ከመቶ ማስመዝገብ ትችላለች ሲሉ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትናንትናው ዕለት በፓርላማ ውሏቸው ገልጸዋል፡፡

አሐዱም የሀገር የምጣኔ ሀብት እድገት የሚለካው በትክክል በምንድን ነው? አስመዘገበች የሚባለው እድገትስ እውን እድገት ነው ብለን መውሰድ እንችላለን ወይ? ሲል የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎችን አነጋግሯል፡፡

የምጣኔ ሀብት ባለሙያው ዶክተር አጥላው አለሙ፤ "ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት (ጂ.ዲ.ፒ) እድገት ሲመዘገብ የተመጣጠነ ሊሆን አልያም ደሃውን የበለጠ ደሀ አድርጎ ሀብታሙን የበለጠ ሀብታም የሚያደርግ ሊሆን ይችላል" ሲሉ ገልጸዋል፡፡

አክለውም፤ "በኢትዮጵያ ያለውም ደሀውን የበለጠ ደሀ ሀብታሙንም የበለጠ ሀብታም የማድረግ አሰራር ነው" ያሉ ሲሆን፤ "የተመጣጠነ እድገት በሌለበት ሁኔታ እድገት ታየ ብሎ ለፖለቲካ ፍጆታ መጠቀም አግባብ አይደለም" ብለዋል፡፡

"ልማትን እና የሀገር ውስጥ ምርት እድገትን መለየት ያስፈልጋል፡፡ ልማት ሲባል የማህበረሰቡ የጤና፣ የትምህርት እና ሌሎችም ፍላጎቶች መሟላቱ መታየት አለበት፡፡ ከሱ ውጭ ሆነው እንቅስቃሴን ብቻ ይዞ ቁጥር መግለፅ ፋይዳ አይኖረውም" ሲሉም አብራርተዋል፡፡

ሌላኛው የምጣኔ ሀብት ባለሙያ ዶክተር ቆስጠንጢንዮስ በርኸ ተስፊ፤ "የሀገር ውስጥ ምርት እድገት ሲለካ ጥቂት ኩባንያዎች ወይም የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሊያስመዘግቡት ይችላሉ፡፡ ይህ ደግሞ የዜጎችን የምጣኔ ሀብት ጤንነት አያመለክትም" ሲሉ ይገልጻሉ፡፡

"ከ200 ቢሊየን ዶላር በላይ በ10 ዓመት ውስጥ ነዳጅ ኤክስፖርት የምታደርገው አንጎላ በድህነት ከሚጠቀሱ ሀገራት መካከል እንድትሆን ያደረጋት የሚመጣው ገንዘብ ማን ኪስ ውስጥ እንደሚገባ ስለማይታወቅ ነው" ብለዋል፡፡

አክለውም፤ እንደ ኢኳቶሪያል ጊኒ እና ደሞክራቲክ ኮንጎ የመሳሰሉት ሀገራት ያላቸው እድገት ጥሩ ነው ቢባልም፤ በጥቂት ባለሃብቶች እጅ ያለ ገንዘብ ለሀገር እድገት መለኪያ ሊሆን ባለመቻሉ አሁንም የከፋ ድህነት ውስጥ መሆናቸውን የገለጹ ሲሆን፤ በዚህም ምክንያት ጥቂቶችን ተጠቃሚ የሚያደርግን እድገት እንደ ሀገር አድርጎ መውሰድ እንደማይገባ ተናግረዋል፡፡

በተጨማሪም "የሀገር ትክክለኛ እድገት የሚለካው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በሚያወጣው የሰው ልማት መረጃ ጠቋሚ (ኤች ዲ አይ) ነው" ያሉት ባለሙያው፤ "ኢትዮጵያ ያላት እድገት ዝቅተኛ ነው" ሲሉም አስረድተዋል፡፡

"የሀገር ውስጥ ምርት እድገት ግን አካታች ባለመሆኑ በምጣኔ ሀብት አደግን ብለን ልንወስደው አንችልም" ሲሉም አክለዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ ያስመዘገበችው እድገት ከፍተኛ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገራቸውም አይዘነጋም፡፡

በእመቤት ሲሳይ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 11:13


በአማራ ክልል ያለው ግጭት ለቀጣናው ስጋት ነው ሲሉ ምሁራን ገለጹ

ጥቅምት 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ አማራ ክልል ያለውን ግጭት ተከትሎ ዜጎች መደበኛ የዕለት ተዕለት ኑሯቸውን ለመኖር በሰላም ወጥቶ መግባት እና መደበኛ እንቅስቃሴዎችን መከወን እንዳልቻሉ ይገለጻል።

"ኢትዮጵያ ብቸኛዋ የሰላም ሚኒስቴር ያላት እንዲሁም ሰላም ማግኘት ያልቻለች ሀገር፤ የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም እያላት ህዝብ የሚያለቅስባት ሀገር ነች" የሚሉት የዲፕሎማሲ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ባለሙያ ጥላሁን ሊበን፤ "ከቀደመው ግጭትና ጦርነት ትምህርት መውሰድ አልተቻለም" ይላሉ።

"አራት ዓመታት የእርስ በእርስ ጦርነትና ግጭት ውስጥ ነበርን" የሚሉት ጥላሁን ሊበን፤ በዚህ ውስጥ በርካታ ዜጎችን ሕይወታቸውን እንዲያልፍ ሆኗል ሲሉ ገልጸዋል።

"በአማራ ክልል ያለው ግጭት በዚሁ የሚቀጥል ከሆነም የአፍሪካ ቀንድ ቀጣና ስጋት ይሆናል" ሲሉም ገልጸዋል።

አሁን ላይ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልል ያለው አለመረጋጋት ወደ ሌሎች ክልሎችም ይዛመታል ያሉ ሲሆን፤ "ከጦርነት የምናተርፈው የወጣትን ሞት ብቻ ነው" ብለዋል።

"በክልሉ ከመንግሥት ጋር በግጭት ውስጥ ያሉ አካላት አላማቸው ምን እንደሆነ፣ 'ያለን አቅም ምን ያህል ነው?'፣ 'ከጎናችን ማን አለ?' የሚሉ ጥያቄዎችን በእውኑ መልሰዋል ወይ?" የሚሉት ደግሞ የቀድሞው አምባሳደር ጥሩነህ ዜናው ናቸው።

እንዲሁም በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማባባስ ከውጭ በእጅ አዙር ተሳታፊ የሆኑ አካላት ሊኖሩ እንደሚችል ጠቁመው፤ "የዜጎችን ችግርና እንግልት ከማራዘም ይልቅ መፍትሔው ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል።

"አሁን ላለው ችግር ተጠያቂ የሚሆኑ የተለያዩ አካላት ቢኖሩም ህዝቡ ግን እየተጎዳ ነው" ብለዋል።

በቀጣናው ያለውን ግጭት እንደመልካም አጋጣሚ የሚወስዱት መኖራቸውንም ታሰቢ ማድረግ እንደሚገባ ገልጸዋል።

የፌደራል መንግሥት የክልል ልዩ ኃይሎች ህልውና አብቅቶ ወደ ፖሊስና እና የመከላከያ መዋቅሮች እንዲካተቱ መወሰኑን ተከትሎ፣ የአማራ ክልል ልዩ ኃይል መፍረስን በመቃውም የተቀሰቀሰው ግጭት ክልሉን ቀውስ ውስጥ መክተቱ ይታወቃል።

በትናንትናው ዕለት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የምክር ቤቱ አባል እና የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አብን ተወካይ የሆኑት ዶ/ር አበባው ደሳለለኝ በክልሉ ስላለው ሁኔታ ላነሱት ጥያቄ፤ "መንግሥት አሁንም ለድርድር እና ምክክር ዝግጁ ነው" ሲሉ ምላሽ መስጠታቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በፍርቱና ወልደአብ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 10:46


በኮንታ ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ6 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ጥቅምት 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኮንታ ዞን አመያ ዙሪያ ወረዳ ጫሬ ቀበሌ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ የሥድስት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የክልሉ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በቀበሌው ትናንት ምሽት የጣለው ከባድ ዝናብ ተከትሎ ዛሬ ጠዋት 2 ሠዓት ላይ የመሬት መንሸራተት መከሰቱን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ሕይወታቸውን ያጡት ሰዎች የሁለት ቤተሰብ አባላት ሲሆኑ፤ ከአንደኛው ቤተሰብ አራት እንዲሁም ከሌላኛው ቤተሰብ ሁለት ሰዎች ሕይወታቸውን እንዳጡ አስረድተዋል፡፡

በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋም ሁለት ቤት የወደመ ሲሆን፤ የነፍስ አድን ሥራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ኢንስፔክተር ደጀኔ ለኤፍቢሲ ተናግረዋል፡፡ እስከ አሁን 1 አስከሬን ተገኝቷል ብለዋል፡፡

በአካባቢው አሁንም መሬቱ እየተናደ መሆኑ እና የውኃ ሙላት (ጎርፍ) መኖሩ የነፍስ አድን ሥራውን በሚፈለገው ልክ እንዳይሆን ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 10:25


#አሐዱ_ትንታኔ

ሩስያ የኒውክሌር ሃይሏን ዝግጁነት ለመፈተሸ ከሁለት ቀን በፊት የተሟላ ልምምድ ማስጀመሯ ተሰምቷል፡፡ የዩክሬኑ ጦርነት አለምን ወደሚያሰጋት የኒውክሌር ጦርነት እንዳይወስዳት ተፈርቷል፡፡

ሩስያ አሁን ያደረገቸው ልምምድ በሁለት ሳምንት ውስጥ ሁለተኛው ነው፡፡ ጉዳዩን በዛሬው አለማቀፍ ትንታኔያችን ተመልክተነዋል፡፡
ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/z-RDlBJR6Fg?si=wa_nKbkV8hYhbDdu

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 09:36


ብሔራዊ ባንክ በባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበት የገንዘብ ገበያ ይፋ አደረገ

ጥቅምት 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባንኮች እርስ በርሳቸው የሚበዳደሩበትን የገንዘብ የግብይት ሥርዓት መፍቀዱን አስታውቋል።

ብሔራዊ ባንኩ ዛሬ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፤ "በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት መጀመር ንግድ ባንኮች የዕለት ተዕለት የገንዘብ ፍሰታቸውን በአግባቡ እንዲያስተዳድሩ ያግዛቸዋል" ብሏል።

በተጨማሪም "የገንዘብ እጥረት ስጋትን በመቀነስና በተረጋጋ የወለድ ተመን ለደንበኞች የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል" ሲል ገልጿል።

ንግድ ባንኮች ብድር መበደር ወይም ማበደር የሚችሉት ለአንድ ቀን ወይም ለሰባት ቀናት ለሚከፈል ገንዘብ ብቻ እንደሆነም አስታውቋል።

ይህም ባንኮች የአጭር ጊዜ የገንዘብ ጉድለትን በመሸፈን ወይም ትርፍ ገንዘብን ለሌሎች ባንኮች በማበደር የገንዘብ ፍሰትን በብቃት እንዲያስተዳደሩ እንደሚያስችል ተመላክቷል።

እንዲሁም በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት በኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋይ ገበያ የግብይት መድረክ ላይ ብቻ እንዲከናወን የተፈቀደ ሲሆን፤ ግብይቱ ላይ ለመሳተፍም ሁሉም የንግድ ባንኮች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፍቃድ ማግኘት እና የሚጠበቅባቸውን መስፈርቶች ማሟላት እንደሚገባቸው ተመላክቷል።

በተጨማሪም ይህ በባንኮች መካከል የሚደረግ የገንዘብ ግብይት የባንክ ዘርፉን በማጠናከር በኢኮኖሚው ዉስጥ ቀልጣፋ የገንዘብ ፍሰት እንዲኖርና የኢኮኖሚ ዕድገት እንዲፋጠን እንደሚያግዝ ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

01 Nov, 08:57


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የተገኙበት መድረክ በመቐለ ከተማ መካሄዱ ተገለጸ

ጥቅምት 22/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በህወሓት አመራሮች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት ለመፍታት ዛሬ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም በሃይማኖት አባቶች የተዘጋጀ መድረክ፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን እና የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ማገናኘቱ ተሰምቷል፡፡

በመቐለ ከተማ በመካሄድ ላይ እንደሚገኘው መድረኩ በህወሓት አመራሮች ላይ የተፈጠር ልዩነት የሕዝብና የሀገርን ጥቅም በሚያስጠብቅ መልኩ ሰላማዊ በሆነ መንገድ አለመግባባቱን እልባት ለመስጠት በማለም የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በመድረኩም ሁለቱም ወገን ጥሩ የሚባል መቀራረብ ማሳየታቸው የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡

ከሁለት ቀናት በፊት የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ በተረጋገጠ የX ገጻቸው ላይ፤ ከዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልጋር ንግግር ማድረጋቸውን በሚመለከት መልዕክት ማጋራታቸው ይታወሳል፡፡

በመልዕክታቸውም፤ "ከሩቅ የሚመጣ ሰው አያስፈልግም ለመቀራረቡ እኛ እንቀርባለን ብላችሁ እኛን ለማገናኘት በመጣር ላይ ያላችሁ ክብር ይስጣችሁ" ያሉ ሲሆን፤ "ተቀራረቦ እንደመነጋገር የመሰለ ነገር የለም" ብለዋል፡፡

በወቅቱም ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ጋር አብረው የተነሱትን ፎቶ ያጋሩ ሲሆን፤ ይህም በሁለቱ መካከል የንግግር ሂደት መጀመሩን አመላካች እንደሆነ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡ የዛሬውም የውይይት መድረክ የዚሁ መቀራረብ አንደኛው አካል እንደሆነ ታምኖበታል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: www.facebook.com/ahaduradio
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 18:11


#አሐዱ_ስንክሳር

ኢትዮጵያ በተለያዩ ወቅቶች የተከሰቱ የታሪክ ምዕራፋትን አልፋለች። እነዚህን የታሪክ እጥፋቶች እየተከታተሉ የሚከትቡ ጸሐፊያንም አሉ።

አሁን ያለችው ኢትዮጵያም ከባለፈችው ኢትዮጵያ የተወለደች በመሆኗ ከቀደመችው ኢትዮጵያ የምትወርሳቸው አያሌ ባሕሪያት አሉ። እነዚህ ባሕሪያት ከወቅታዊዉ የኢትዮጵያ ሁኔታ ጋር ሆነውም ዛሬ የምናያትን ኢትዮጵያ ይገልፃሉ።

ታሪክ ግን፣ የኋላ ማንነትን ማሳያ መስታወት ሆኖ በማገልገል ወደ ፊት እንዴት መጓዝ እንዳለብን ያሳስበናል።

ታሪክ ዘጋቢዎች የተከሰቱ እና የተፈፀሙ ዕውነቶችን በስርአት ጽፈው እንዲያሻግሩም ኃላፊነት አለባቸው። በዛሬው ኢትዮጵያዊ ስንክሳራችን የሐገሪቱን ታሪካዊ ጉዞዎችን ከጸሐፊያን አንፃር እንቃኘዋለን።

በጥበብ በለጠ
ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/1vQQTb6A2OE?si=gM3EI1JcBfCFXb5A

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 15:28


የመኖ የዋጋ ጭማሪ ወደ ውጭ አገራት የሚላከው የስጋ ንግድ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አሳድሯል ተባለ

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጽያ ከዓመታት በፊት ጥሩ የገቢ ምንጭ የነበረው የስጋ ምርት አሁን ላይ በተለያዩ ችግሮች ሳቢያ እየተቀዛቀዘ መምጣቱን ተገልጿል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከስጋ ምርት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያለው የመኖ አቅርቦት በአገር ውስጥ አቅርቦት መቀዛቀዙና ዋጋው አልቀመስ እያለ መምጣቱን ተከትሎ፤ የወጪ ንግድ ላይ አሉታዊ ጫና ማሳደሩን ተነግሯል።

ለዚህም እንደምክንያት የሚነሳው የአቅርቦች ችግር መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ተፈጠረ የተባለውን ችግር ለማቃለል በብርቱ እየተሰራበት መሆኑን የሚታወቅ ቢሆንም፤ ችግሩን መፍታት አዳጋች እንደሆነበት ሚኒስቴር መስርያ ቤቱ ገልጿል።

በግብርና ተረፈ ምርትን ተጠቅመው መኖ የሚያመርቱ ድርጅቶችና ወደ ዘርፉ የሚገቡ የምጣኔ ሐብት አከናዋኞች ማግኘት እየተቻለ ባለመሆኑ ችግሩ መከሰቱንም ሚኒስቴሩ እንደምክንያት አንስቷል።

በዋነኝነት መኖ ማቀነባበርን ጨምሮ ተረፈ ምርትን ወደ ጥቅም የሚያውሉ አጋዥ የግሉ ዘርፍ ተዋናያን ችግር ከመሆኑ በተጨማሪም፤ በቅርቡ ደግሞ በእንስሳት መኖ ላይ የተስተዋለውን የዋጋ ጭማሪ ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ አገራት የሚላከው የስጋ ንግድ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እያሳደረ መምጣቱ ተገልጿል።

ሚኒስተሩ ይህንን እየተስተዋለ ያለውን ችግር ለማሻሻል በርካታ ሥራዎች እየሰራ ቢሆንም፤ ችግሩን በሚፈለገው ልክ ማቃለል እንዳልተቻለ አስታውቋል።

ይህንን ለአሐዱ የነገሩት፤ በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና አሳ ልማት ሀብት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ፅጌሬዳ ፍቃዱ ናቸው።

መሪ ሥራ አስፈፃሚዋ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ወደ ውጭ አገራት የምትልከው የሥጋ ምርት መልካም በሚባል ደረጃ የነበረ ቢሆንም፤ አሁን ላይ እየተቀዛቀዘ መሆኑን ለአሐዱ ተናግረዋል ።

ችግሩን ለመቅረፍም እየተሰራበት መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ስጋ ላኪዎች ማህበር "በስጋ አቅቦት እጥረት የተነሳ ሥራችን ላይ ተፅእኖ እየፈጠረብን ነው" ሲሉ መቆየታቸውም አይዘነጋም።

ኢትዮጵያ በርካታ የእንስሳት ሐብት የበለፀገች መሆንዋን በተደጋጋሚ ሲነገር ቢቆይም፤ ዘርፉን ከገጠመው ከችግር መላቀቅ እንደተሳነው እየተነገረ ይገኛል።

በአማኑዔል ክንደያ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 15:14


በነዳጅ ታንከር ተደብቆ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 11 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ መያዙን ተገለጸ

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በነዳጅ ታንከር ውስጥ ተደብቆ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 11 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከመሰል ዘጠኝ ካዝና እና ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር መያዙን ገልጿል።

ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያው ሊያዝ የቻለው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ባገኘው መረጃ መሰረት መሆኑ ተመላክቷል።

በዚህም ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም መነሻውን ጋምቤላ ክልል አድርጎ ወደ አማራ ክልል ለማስገባት ታስቦ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 11 ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከመሰል ዘጠኝ ካዝና ጋር ከፋ ዞን ቦንጋ ከተማ ሲደርስ በተደረገው ጥብቅ ክትትል የተጠረጠረው ተሽከርካሪ አካል ተፈትሾ ሊገኝ ባለመቻሉ የፖሊስ ሙያተኛን በመጨመር የነዳጅ ታንከር ወርዶ ውስጡ እንዲፈተሽ በመደረጉ መያዙ ተነግሯል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 13:59


በግጭቶች እና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት 5 ሺሕ 568 ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን ተገለጸ

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ በሚገኙ የተለያዩ ክፍሎች በተከሰቱ እና በቀጠሉ ግጭቶች እንዲሁም በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት 5 ሺሕ 568 ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገለጸ፡፡

ኮሚሽኑ ዛሬ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም የማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ያተኮረ ባለ 25 ገጽ ዓመታዊ ሪፖርት አውጥቷል።

በሪፖርቱም በትግራይ ክልል 105 ገደማ ትምህርት ቤቶች በጦርነት በመውደማቸውና የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ በመሆናቸው ምክንያት ተገቢውን አገልግሎት እየሰጡ አለመሆኑን ገልጿል።

እንዲሁም ተፈናቃዮች በሚገኙባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 52፣ በአፋር ክልል 17፣ በአማራ ክልል 14፣ በኦሮሚያ ክልል 11፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 11 እና በጋምቤላ ክልል 11 ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን አስታውቋል።

ኢሰመኮ በሰኔ ወር እና ሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም. ባሰባሰበው መረጃ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በተከሰቱ እና በቀጠሉ ግጭቶች እንዲሁም በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት፤ በአማራ ክልል 4 ሺሕ 178፣ በትግራይ ክልል 648፣ በኦሮሚያ ክልል 420፣ በሶማሊ ክልል 195፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 50፣ በጋምቤላ ክልል 40፣ በአፋር ክልል 26 እንዲሁም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል 8 ትምህርት ቤቶች መዘጋታቸውን በሪፖርቱ አመላክቷል፡፡

የጸጥታ ሁኔታው አንጻራዊ መሻሻል ባሳየባቸው አካባቢዎች ደግሞ መምህራን አካባቢውን ለቀው የሄዱ በመሆናቸው የመምህራን እጥረት መኖሩን የገለጸው ኮሚሽኑ፤ በአካባቢዎቹ አስተማማኝ ጸጥታ ባለመኖሩ ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት እንደማይልኩ አስታውቋል።

በተጨማሪም "በአንዳንድ አካባቢዎች መምህራን ትምህርት ቤት ውስጥ ለመገኘት በተለይም ሴት መምህራን የመደፈር እና የመዘረፍ ሥጋት ያለባቸው በመሆኑ ትምህርት ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል" ሲል ገልጿል።

ኮሚሽኑ በተጨማሪ የጤና ጉዳዮችንም በሪፖርቱ ያነሳ ሲሆን፤ "ባለሙያዎች ደመወዝ ወቅቱን ጠብቆ በአግባቡ ባለመከፈሉ ሳቢያ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች የሕክምና አገልግሎት እንዲስተጓጎል ምክንያት ሆኗል" ብሏል።

በተጨማሪም "የመድኃኒት እጥረት እና በግጭት ምክንያት የጤና ተቋማት በቂ አገልግሎት እየሰጡ ባለመሆናቸው ችግሩ ተባብሶ ቀጥሏል" ሲል ገልጿል፡፡

ኮሚሽኑ አክሎም በአማራ ክልል ያለው የትጥቅ ግጭት ምክንያት የተለያዩ የጤና ተቋማት ሥራቸውን በአግባቡ እንዳይሠሩ ከማድረጉ በተጨማሪ፤ የሕክምና መሣሪያ፣ መድኃኒት፣ ደም፣ ኦክስጂን እና ሌሎች ግብአቶች አቅርቦት እጥረት እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑንም አመላክቷል።

ኢሰማኮ በሪፖርቱ መንግሥት በትጥቅ ግጭትም ሆነ በተፈጥሮ አደጋ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ አስቻይ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እርምጃዎችን እንዲወስድ ጠይቋል።

የወደሙ ትምህርት ቤቶች እንዲገነቡ እና መልሰው እንዲቋቋሙ ለማድረግ በቂ በጀት ተይዞላቸው በዕቅድ ውስጥ መካተታቸውን እንዲያረጋግጥ የጠየቀው ኢሰመኮ፤ ትምህርት ቤቶቹ መደበኛ አገልግሎት መስጠት እስኪጀምሩ መንግሥት ጊዜያዊ የመማሪያ አማራጮችን ጨምሮ የተለያዩ መፍትሔዎችን እንዲያመቻች እንዲሁም አስፈላጊ የትምህርት ቁሳቁሶችን እንዲያሟላሜ አሳስቧል።

በተጨማሪም በትጥቅ ግጭት ሳቢያ የወደሙትን መሠረተ ልማቶች በመጠገንና አገልግሎቶችን በፍጥነት ወደ ሥራ በማስገባት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ መብቶች በተሻለ ሁኔታ የሚረጋገጡበትን መንገድ እንዲያመቻች ኮሚሽኑ ምክረ ሃሳቡን ሰጥቷል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 13:00


#አሐዱ_ትንታኔ

አሜሪካ በታይዋን ጉዳይ ጣልቃ መግባቷን እንድታቋርጥ ቻይና አስጠንቅቃለች፡፡ ቤጂንግ በበኩሏ እንደራሷ አንድ አካል በምትቆጥራት ታይዋን ላይ አሜሪካ ጣልቃ መግባቷ ተቀባይነት የለውም ብላለች፡፡ 

አሜሪካ ለምን ታይዋንን ፈለገች የሚለውን በዛሬው የዓለም አቀፍ ትንታኔያችን ተመልክተነዋል።

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/sZdWUTv7JOg?si=yBztf_zKV9D1ouAe

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 12:09


የጸጥታ አካላት ትዕዛዝ ባለመቀበላቸዉ ሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድን መቆጣጠር አልተቻለም ተባለ

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በሁሉም ዞኖችና ከተማ አስተዳደሮች በሚባል ደረጃ አንድ ሊትር ቤንዚን በሕገወጥ መንገድ ከ250 እስከ 300 ብር እየተሸጠ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል።

አሐዱም ለምን በዘላቂነት ችግሩን መቅረፍ እና ሕገወጥነትን መቆጣጠር አልተቻለም ሲል፤ የክልሉን ንግድና ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊና የኮምኒኬሽን ዳይሬክተር ሳሙኤል ሳዲሁን ጠይቋል።

በምላሻቸውም መሰል ችግሮች በክልሉ ብቻ ሳይሆን ሀገር አቀፍ ደረጃ መሆኑን ተናግረዋል።

በዋነኛነትም የጸጥታ አካላት የቁጥጥር ባለሙያዎችን ትዕዛዝ አለመቀበል እንዲሁም፤ በሕገወጥ ሥራው ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ጋር በጋራ በመስራታቸው እና በሌሎች ምክንያቶች ሕገወጥ እግዱን መቆጣጠር እንዳልተቻለ ተናግረዋል።

ኃላፊው አያይዘውም ችግሩ አሽከርካሪዎችንና የህብረተሰብ ክፍሎችን ለእንግልት እየዳረገ መሆኑን ተናግረዋል።

ከሚመለከታቸው ከፌዴራል መስሪያ ቤቶች ጋር በቅንጅት በመሥራት ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እየሰራ ነው ሲሉም ገልጸው።

የቁጥጥር ሥራዎችን በማጠናከር በክልሉ የተከሰተውን ሕገወጥ ተግባር በቅርብ ጊዜ ውስጥ ይቀረፋል ሲሉም ጠቁመዋል።

በወልደሀዋርያት ዘነበ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 10:55


ሶማሊላንድ ከየትኛውም ወገን ተቃውሞ እና ጫና ቢመጣ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን ስምምነት ተግባራዊ ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማትል ገለጸች

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሶማሊላንድ ከየትኛውም ወገን ተቃውሞ እና ጫና ቢመጣ ከኢትዮጵያ ጋር የገባችውን ስምምነት ተግባራዊ ከማድረግ ወደ ኋላ እንደማትል የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንት ሙሳ ቢሂ ይህን የተናገሩት ከሁለት ሳምንት በኋላ በሶማሊላንድ ከሚካሄደው ምርጫ ጋር በተያያዘ ከቢቢሲ ሶማሊኛ አገልግሎት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።

በቃለ ምልልሱ ላይም አገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር በደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት እና በቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

በዚህም የመግባቢያ ስምምነቱ "ምንም ነገር ሳይቀየር በነበረበት እንዳለ ነው።" ያሉት ፕሬዝዳንቱ፤ "በመግባባት ደረጃ ላይ ነው ያለው። ሁሉም ወገን የተግባራዊነት ሰነዱ መቼ እንሚፈረም እየተጠባበቀ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

የመግባቢያ ስምምነቱ ከተፈረመ በኋላ ውዝግብ መፈጠሩን ያመለከቱት ቢሂ፤ "ኢትዮጵያ ለምን ከሶማሊላንድ ጋር ስምምነት ተፈራረመች" በሚል የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ኢትዮጵያ ላይ ዘመቻ መክፈታቸውን ተናግረዋል።

ስምምነቱ ከሶማሊያ ግዛት ጋር ሳይሆን ራሷን ከቻለች አገር ሶማሊላንድ ጋር የተደረገ መሆኑን በመግለጽም፤ "ፕሬዝዳንት ሐሰን "የእኛ ነው" ወደሚሉት መሬት መሄድም ሆነ መቆጣጠር እንደማይችሉ ያውቁታል" ብለዋል።

"ለ34 ዓመታት ሁለት የተለያየን ነጻ አገራት ነን፤ ሁለት መንግሥታት ነን፤ ሁሉም ያውቀዋል" ሲሉም ተናግረዋል።

አክለውም፤ ከስምምነቱ በኋላ አለመግባባቱ መካረሩን በመጥቀስ “ጦርነት ታቅዶ ነበር። ግብፅ እንድትገባበት ተደረገ፤ ውዝግብ ተፈጠረ። ይህ ተጨማሪ ነገር ነው፤ መፍትሄም አይሆንም" ብለዋል።

"ፕሬዝዳንት ሐሰን ሁለት የተለያየን መንግሥታት መሆናችንን ከተረዳ እና ከእኛ ጋር ንግግር ከፈለገ መልካም ነው" ሲሉም፤ ሶማሊያ አገርነታቸውን ከተቀበለች ለንግግር በራቸው ክፍት መሆኑን አመልክተዋል።

ፕሬዝዳንቱ ጨምረውም ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ በሶማሊላንድ መሬት የሚመለከታቸው ነገር አለመኖሩን ጠቅሰው፤ "ለኢትዮጵያ መሬት ሰጡ" በማለትም የሚናገሩት የማይመለከታቸውን ጉዳይ ነው" ሲሉ አጣጥለውታል።

"ኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ሶማሊዎች አሉ፤ በመንግሥት ውስጥም ቦታ ያላቸው ናቸው። ታዲያ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ተፈራረማችሁ በማለት ሶማሊያ ለምንድን ነው የምትከሰን?" ሲሉም ጠይቀዋል።

"ሶማሊያ ከግብፅ ጋር የደረሰችው የወታደራዊ ትብብር ስምምነቱ የሶማሊላንድ ሕዝብ የነጻ አገርነት ፍላጎትን ለማስቆም የታለመ ነው" ብለው እንደሚያምኑም ተናግረዋል።

በአንድ ወር ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የኢትዮጵያ እና የሶማሊላንድ ስምምነት አንድ ዓመት ሊሞላው ሁለት ወራት ቀርተውታል።

ነገር ግን የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት እንደሚሉት መዘግየቱ ጉዳዩ ሰፊ ጊዜን የሚጠይቅ እና ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ወደ ተግባር ለመቀየር በርካታ ዓመታትን የሚጠይቁ መሆናቸውን በምሳሌነት አንስተዋል።

በሶማሊያ በኩል የተደረገ ጫና በስምምነቱ መዘግየት ላይ ምንም ሚና እንደሌለው የገለጹም ሲሆን፤ "የመግባቢያ ስምምነቱ የራሱን ጊዜ እየተከተለ ነው። የመጨረሻውን ሁለቱ አገራት የሚወስኑት ይሆናል" በማለት፤ ጉዳዩ በኢትዮጵያ እና በሶማሊላንድ እጅ ላይ ያለ መሆኑን ተናግረዋል።

አክለውም ከሶማሊያ ጋር የወታደራዊ ትብብር ስምምነት የተፈራረመችውን ግብፅን በተመለከተ፤ "ግብፅ ከኢትዮጵያ ጋር ባለባት የአባይ ውሃ ውዝግብ ውስጥ ሶማሊያን በማስገባት እየተጠቀመችባት ወደ ጦርነት ልታስገባት ነው" ብለዋል።

"የራሷ ችግር አለባት ያሏትን ግብፅ የሶማሊያ መንግሥት ወደ ቀጣናው ውዝግብ ማስገባቱ ትክክል አይደለም" ያሉት ቢሂ፤ "የወታደራዊ ስምምነቱ ግብፅ ከኢትዮጵያ ጋር ካለባት ውዝግብ በተጨማሪ በሶማሊላንድ ላይ ጭምር ያነጣጠረ ነው" ሲሉ ከሰዋል።

ፕሬዝዳንቱ ከኢትዮጵያ ጋር ስምምነት ከመፈራረማቸው በፊት ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ መሐሙድ ጋር በተገናኙበት ጊዜ ይህንኑ አስረግጠው እንደነገሯቸው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ነጻ አገርነቷን ካወጀችው ሶማሊላንድ የባሕር በር፣ ሶማሊላንድ ደግሞ የአገርነት ዕውቅናን ለማግኘት የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረሙ በኋላ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያለው የፖለቲካ ትኩሳት ከተጋጋለ አንድ ዓመት ሊሞላው ነው።

ስምምነቱ ከተደረሰ በኋላ ሶማሊያ ተቃውሟዋን እያሰማች ሲሆን፣ ኢትዮጵያንም ሉዓላዊነቷን በመጣስ ከመክሰስ ባሻገር ከኢትዮጵያ ጋር ውዝግብ ውስጥ ከምትገኘው ግብፅ እና ግንኙነታቸው እየሻከረ ካለው ከኤርትራ ጋር ዘርፈ ብዙ የትብብር ስምምነት መፈራረሟ ይታወሳል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 09:20


"የፍርድ ሂደቶች የፖለቲካ በቀል መፈፀሚያ መሆን የለባቸውም" የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ እየተካሄዱ የሚገኙ የፍርድ ሂደቶች የፖለቲካ በቀል መፈፀሚያ መሆን የለባቸውም ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል አሳስቧል።

ሕጉ የዋስትና መብት ጭምር የማይነፍግባቸው ክሶች ለተራዘመ የእስር ቆይታና እንግልት እየተዳረጉ መሆኑን የሕግ ባለሙያዎችና ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ገልጸዋል፡፡

ከፖለቲካ ጋር የተያያዘ ነው የሚባሉ ክሶችን የተቀመጠውን ሕግ በመጣስ ጭምር ያላግባብ ዜጎችን ለእንግልት እየዳረገ መሆኑም ተነስቷል፡፡

"ከዚህ ባለፈም በተደጋጋሚ ግዜ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እየተባለ የማጉላላትና እና ማራዘም ተገቢ አይደለም" ሲሉ ለአሐዱ የተናገሩት የሕግ ባለሙያውና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ሃይለማርያም ናቸዉ፡፡

"ሕጉን ለማስተማሪያነትና ፍትህን ለማስረፅ ሳይሆን ሕጉን የመንግሥት ባለስልጣናት በበቀል ተነስሳተው እንደሚጠቀሙበት ማድረግም ተገቢ አይደለም" ብለዋል፡፡ አክለውም በአሁኑ ወቅት እንደሚስተዋለው የፍርድ ሂደቶች የፖለቲካ በቀል መፈፀሚያ መሆን የለባቸውም ሲሉም ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የአስቸኳይ ግዜ አዋጅን ምክንያት በማድረግ ጋዜጠኞች እና ፖለቲከኞችን ጨምሮ የተለያዩ አካላት በሕገ ወጥ መንገድ በእስር ላይ እንደሚገኙ በበርካታ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ሲገለጽ ቆይቷል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ባሳለፍነው ሳምንት ባወጣው ሪፖርት፤ በአዲስ አበባ ከተማ፣ እንዲሁም በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች የተለያዩ አካባቢዎች የአስገድዶ መሰወር እና ያሉበት ሳይገለጽ በተራዘመ እስር ሁኔታ ውስጥ የሚቆዩ ሰዎች መበራከታቸውን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

በአቤል ደጀኔ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 08:44


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ በፓርላማ ከምክር ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ማብራሪያ ይሰጣሉ

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ነገ ጥቅምት 21 ቀን 2017 ዓ.ም. በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለሚነሱላቸው ጥያቄ ምላሽ እንደሚሰጡ ታውቋል፡፡

በዚህም በመስከረም 2017 ዓ.ም. መጨረሻ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የመጀመሪያ ስብሰባ፣ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሆነው የተሰየሙት ታዬ አጽቀሥላሴ በመንግሥት የዘንድሮ ዕቅድ ላይ ባደረጉት ንግግር ላይ የምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥያቄ ያቀርባሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለከፍተኛ የመንግሥት ሃላፊነት ቦታዎች ሹመት እንዲፀድቅላቸው በደብዳቤ ባቀረቡት ጥያቄ መሰረት፤ ትናንት በተከናወነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ የ5 ሚኒስትሮች ሹመት መጽደቁ ይታወሳል፡፡

ነገር ግን ይህ ሹመት በተለይም በቀድሞ የፍትህ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞትዬስ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሆኖ መሾም፤ በምክር ቤት አባላቶች በኩል ከግልጽነት እና ከተጠያቂነት መርህ አንጻር ከፍተኛ ጥያቄ ተነስቶበታል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ የምክር ቤቱ አባላት ጥያቄ ላይም ምላሽ ይሰጡበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

30 Oct, 08:22


በወላይታ ዞን በደረሰ የመሬት ናዳ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ

ጥቅምት 20/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ በትናንትናው ዕለት ማታ ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

በወረዳው ኮይሻ ላሾ ቀበሌ ሞግሳ ቀጠና በተከሰተው መሬት ናዳ የአራት ሰው ሕይወት ያለፈ ሲሆን፤ በ01 ቀበሌ ደግሞ ሦስት ሰው በአጠቃላይ የ7 ሰው ሕይወት ማለፉን አሐዱ ለማወቅ ችሏል።

አደጋው የአንድ ቤተሰብ አባላት ሙሉ በሙሉ እንዲሁም ሌሎች ሰዎች ላይ አደጋ ማድረሱ የተገለጸ ሲሆን፤ በንብረት ላይም ጉዳት አድርሷል።

ከዚህ ቀደም በካዎ ኮይሻ ወረዳ ጤፓ ቀበሌ በመሬት ናዳ ምክንያት የተፈናቀሉትን መልሶ ለማቋቋም ስሰራ ቢቆይም፤ ተደጋጋሚ አደጋ በመከሰቱ ችግሩ እያባባሰው መምጣቱ ተመላክቷል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

27 Oct, 06:00


መልካም ቀን!
አሐዱ ሬድዮ 94.3  የኢትዮጵያውያን ድምፅ!

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 17:21


#አሐዱ_መልህቅ

ጥንቅሩን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/2LsI3elAMks?si=vKFOxJ4gGTtZ1pRB

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 15:43


ፖለቲካን እንደ ገቢ ማግኛ ዘዴ የሚመለከቱ በመኖራቸው ከፓርቲ ፓርቲ የሚቀያይሩ ፖለቲከኞች በዝተዋል ተባለ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ፖለቲከኞች ፍላጎታቸው ስልጣን በመሆኑ አንድ ፓርቲ ላይ የመፅናት ፍላጎት የላቸውም ሲሉ፤ የዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኝ እና ዲፕሎማት አቶ ጥላሁን ሊበን ተናግረዋል፡፡

"በሀገራችን ያሉ ፖለቲከኞች ለአቋቋሙት ፓርቲ ተማኝ የመሆን ብሎም የሚቋቋሙትን ፓርቲ መጠቀሚያ እያደረጉት በመሆኑ አንድ ፓርቲ ላይ መፅናት አይችሉም" ሲሉ ነው አቶ ጥላሁን የገለጹት፡፡

"የዘር ፖለቲካ ላይ የሚያተኩሩ ፓርቲዎች ጭምር ለቆሙለት ብሔር ሳይሆን ለስልጣን እና ጥቅም ያደሉ በመሆናቸው ለፓርቲዎቻቸው ታማኝነት የላቸውም" ሲሉም ተናግረዋል፡፡

"ጥያቄው የስልጣን ነው" የሚሉት አቶ ጥላሁን፤ በዚህ መንገድ አንዱ መንገድ ሲዘጋባቸው ሌላኛውን መንገድ እንደሚፈልጉ አስረድተዋል፡፡ ለዚህም በመንግሥት መዋቅር ውስጥ እየሰሩ ያሉ ተቃዎሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን ጠቅሰዋል፡፡

"ለዚህ መፍትሄው ስልጣንን የሀብት ምንጭ እንዳይሆን ተደርጎ መሰራት አለበት" ያሉት አቶ ጥላሁን፤ ማንኛውም ፖለቲከኛ ፖለቲካን ከጥቅም አኳያ እንዳይመለከት መደረግ እንዳለበትም አመላክተዋል፡፡

ፖለቲካን ንግድ አድርጎ ከማሰብ የሚደረግ ሥራዎች ማስተካከል የሚገባ መሆኑንም የዓለም ዓቀፍ ግንኙነት ባለሙያው ጨምረው ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

"በፖለቲካ ፓርቲ ውስጥ የውስጥ ፖለቲካ ልዩነት ካለ እንዲሁም የርዕዮት ዓለም ልዩነት ከተደረገ ከፓርቲ ፓርቲ መቀየር ግዴታ ሊሆን ይገባል" የሚሉት ደግሞ የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ፓርቲ የዶክመንት ዝግጅት ቡድን መሪ አቶ ቸርነት ሰዒድ ናቸው፡፡

ይሁን እንጂ የርዕዮተ ዓለም ልዩነት ብቻ ፓርቲ ለመቀየር ምክንያት አይሆንም የሚሉት አቶ ቸርነት፤ "የምትቆይበት ፓርቲ ከመርህ እየወጣ ከሆነና የመታገያ ቦታው እየጠበበ ከሆነ የተሻለ ምህዳር ወዳለው ፓርቲ መዞር ችግር አይኖረውም" ሲሉም ገልጸዋል፡፡

የንጋት ኮከብ ለኢትዮጵያ ፓርቲ ከሌሎች የተለያዩ ፓርቲዎች የተሰባሰቡ ፖለቲከኞች የሚገኙበት መሆኑን የሚያነሱት አቶ ቸርነት፤ "በፓርቲዎች ላይ የነበሩ ችግሮችን ቀርፎ በአዲስ መንገድ ለመምጣት እየሰራ ያለ ፓርቲ ነው" ሲሉ ከአሐዱ ጋር በነበራቸው ቆይታ ተናግረዋል፡፡

በአቤል ደጀኔ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 15:15


https://youtu.be/zsvl8nQ6PzY?si=7ErAos4GtsCp42Y5

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 14:51


የጊዳ አያና ወረዳ አንዶዴ ዲቾ ቀበሌ ነዋሪዎች "ማንነትን ማዕከል ያደረገ የከፋ እልቂት ከፊታችን ተደቅኗል" ማለታቸው ተገለጸ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በምሥራቅ ወለጋ ዞን፣ ጊዳ አያና ወረዳ አንዶዴ ዲቾ ቀበሌ "ማንነትን ማዕከል ያደረገ የከፋ እልቂት ከፊታችን ተደቅኗል፤ ድምፃችንን አሰሙልን" ሲሉ የአካባቢው ነዋሪዎች መማጸናቸውን እናት ፓርታ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።

ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም ከአንድ የፀጥታ ኃይል አዛዥ ጋር ከጠዋቱ 4 ሰዓት እስከ 11 ሰዓት ድረስ እንደ ተደረገ በተገለጸ እጅግ ውጥረት የተሞላበት ውይይት፤ የቀበሌው ነዋሪዎች መሣሪያቸውን እንዲያወርዱ ካልሆነ ግን የከፋ ነገር እንደሚጠብቃቸው መገለጹን ፓርቲው መረጃ ደርሶኛል ብሏል።

አዛዡ "ካላወረድክ ... ትታረሳለህ" ማለታቸው የተገለጸ ሲሆን፤ ይህም ነዋሪዎቹ ላይ እጅግ ሥጋት እንዳሳደረባቸው ነው ፓርቲው የገለጸው።

ሥጋቱ ይህ ብቻ ሳይሆን "እኛ መሣሪያ ካወረድን በሰዓታት ልዩነት ሸኔ መጥቶ ይጨፈጭፈናል፤ ይህ ደግሞ ያለፉ ዓመታት የቀን ተቀን ሰቀቀናችን እንደሆነ ማንም ያውቃል" ሲሉም ነዋሪዎቹ መግለጻቸው ተመላክቷል።

"መተማመን በሌለበትና እስከዛሬ ማን አሳልፎ እንደሚሰጠን ባወቅንበትና አሁን በጥቂቱ በመንግሥት ጥረትም፣ በሬያችንን እየሸጥንም ገዝተን በታጠቅነው መሣሪያ ራሳችንን ለማትረፍ የአልሞት ባይ ተጋዳይ በምናደርግበት ወቅት እንዲህ መባሉ እጅግ አስገርሞናል" ብለዋል።

በአካባቢው በግምት 20 ኪ.ሜ ርቀት ላይ መንግሥት ሸኔ ብሎ የሚጠራውና ራሱን ኦ.ነ.ሰ የሚለው ኃይል ከፍተኛ እንቅስቃሴ የሚያካሂድበት ቦታ መሆኑንና እስከ አሁንም በጥቂቱም ቢሆን በዚሁ መንገድ ራሳቸውን እየተከላከሉ እንደቆዩም ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

በጭንቀት ያሉት እነዚሁ የአንዶዴ ዲቾ ቀበሌ ነዋሪዎች ለሞት አሳልፎ የሚሰጠንን ውሳኔ "ብትቀበሉ ተቀበሉት" መባሉ አስገራሚ ነው ማለታቸውን እናት ፓርታ በመግለጫው አመላክቷል።

"እጅግ ውጥረት የተሞላበት ውይይት ነበር። እባካችሁ መሐል ላይ ያለ የእኛን ደህንነት የሚያስጠብቅ መፍትሔ ስጡን" እያልን ብንማጸናቸውም ሊረዱን ዝግጁ አልነበሩም፤ ብቻ 'ታወርዳለህ ታወርዳለህ' እያሉ ይዝቱ ነበር" የሚሉት ነዋሪዎች "በመጨረሻም ባለመግባባት ሕዝቡም አዳራሹን ጥሎ ወጥቷል" ብለዋል።

"በሰሜኑ ጦርነት ወቅት መላው የጸጥታ ኃይል አካባቢውን ሲለቅ መንግሥት እኛን አምኖ ራሳችንን እየተከላከልን አካባቢውንም እንድንጠብቅ ያደረገ ቢሆንም አሁን ምን ተገኝቶ ቃሉን አጠፈ" ሲሉ መጠየቃቸውም በመግለጫው ተመላክቷል።

ፓርቲው ውይይቱን የመሩት የጸጥታ ኃይል ሥምና ማዕረግ እንደደረሰው የገለጸ ሲሆን፤ "በብዙ ምክንያቶች ለጊዜው መጠቀም አላስፈለገንም" ብሏል።

ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለው መሆኑን የገለጸው እናት ፓርቲ፤ የባሰ ዘግናኝ እልቂት ከመፈጸሙ በፊት በተለይ የመከላከያ ሠራዊት አመራሮች ጉዳዩን በገለልተኝነትና ከነባራዊ ሁኔታ ጋር የተገናዘበ መፍትሔ እንዲሰጡት አሳስቧል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 14:19


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አዲሱን የመቐለ ከንቲባ ከሥራ አገዱ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ አዲሱን የመቐለ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ ከሥራ ማገዳቸው ተሰምቷል።

በፕሬዝዳንቱ ትላንት ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም በተፃፈ  ደብዳቤ፤ አዲሱ የመቐለ ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ ሕጋዊ ያልሆነ ተግባራቸውን እንዲያቆሙ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

"የመቐለ ከተማ ምክር ቤት መጠቀምያ በማድረግ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ሥራ የሚፃረር ተግባር መፈፀም አይቻልም " ያለው የፕሬዝዳንቱ ደብዳቤ፤ የአዲሱ ከንቲባ ሹመት በጊዚያዊ አስተዳደሩ ተቀባይነት እንደሌለው አስረድቷል።

አቶ ጌታቸው በደብዳቤው "የጊዚያዊ አስተዳደሩን የሚፃረር አቋም በመያዝ በጊዚያዊ አስተዳደሩ ሥር ያለን መዋቅር መምራት አትችሉም" ያሉ ሲሆን፤ "ጊዚያዊ አስተዳደሩም ከእርስዎ ጋር መሰራት አይችልም" ሲሉም አሳስበዋል።

በመቐለ ከተማ የሚገኙ የመንግሥት መዋቅሮች "ሕጋዊ አይደሉም" የተባሉት ከንቲባ የሚሰጡዋቸው አመራሮች እና ትዕዛዞች ተቀብለው እንዳይፈፅሙም ፕሬዝዳንቱ አስጠንቅቀዋል።

አዲሱ የመቐለ ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ በርሀ፤ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመሩት ህወሓት የሥራ አስፈፃሚ ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 13:27


በመዲናዋ 120 የሚሆኑ የመድሀኒት መደብሮች ላይ ፈቃድ እስከመዘረዝ የደረሰ እርምጃ መወሰዱ ተገለጸ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ከ1 ሺሕ 6 መቶ የመድሀኒት መደብሮች ዉስጥ 120 የሚሆኑት ላይ ፈቃድ እስከመዘረዝ የደረሰ እርምጃ እንደተወሰደባቸዉ የአዲስ አበባ ከተማ ምግብ እና መድሃኒት ባለስልጣን አስታውቋል፡፡

ባለስልጣኑ በ50 መድሃኒት መደብች ላይ ጊዜያዊ እግድ እንዲሁም በ70 መድሃኒት መደብሮች ላይ የጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እርምጃ መወሰዱን ለአሐዱ ገልጿል።

ጊዜያቸው ያለፈ መድሃኒቶችን መሸጥ እንዲሁም ከመድሃኒት አቀማመጥ እና የመድሃኒቶች አያያዝ ላይ ቁጥጥር በማድረግ በመድሃኒት መደብሮች ላይ እርምጃ እንደተወሰድባቸው ተነግሯል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ከ1 ሺሕ 6 መቶ በላይ መድሃኒት መደብሮች ሕጋዊ ሆነው አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ ለአሐዱ የተናገሩት፤ በባለስልጣኑ የጤና ተቋማት እና ባለሙያዎች ቁጥጥር ዳይሬክተር አቶ ገልገሎ ኦልጅራ ናቸው፡፡

ተቋሙ የመድሃኒት አቀማመጥ፣ የመድሃኒት መደብሩን የክፍሉ የሙቀት መጠን፣ ፍቃድ ያለው ግለሰብ ስለመኖሩ እንዲሁም ስለሚሸጡት መድሃኒት ለደንበኛ በግልጽ የማስረዳት እና ሌሎችን ጉዳዮች እንደሚከታተሉ ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

በቅድሚያ ለመድሃኒት መደብሮች የማስተማር እንዲሁም በክትትል ወቅት የሚስተዋሉ ስህተቶችን የቅድመ ማስጠንቀቂያ ሥራ እንደሚሰጥም ጨምረው አስረድተዋል፡፡

በማስጠንቀቂያ የማይታረሙ መድሃኒት መደብሮች ላይ እስከ ፈቃድ የመሰረዝ አስተዳደራዊ እርምጃ የሚከናወንበት ሁኔታ ስለመኖሩ ተመላክቷል።

በእሌኒ ግዛቸው

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 13:14


በሩብ ዓመቱ ከታቀደው 100 ሺሕ ዩኒት ደም ውስጥ 94 ሺሕ ዩኒት ደም መሰብሰቡ ተገለጸ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በተያዘው ሩብ ዓመት ሦስት ወራት፤ በደም ማሰባሰብ ሂደት ከታቀደው 100 ሺሕ ዩኒት ውስጥ 94 ሺሕ የሚሆን ዩኒት ደም መሰብሰብ መቻሉን የኢትዮጵያ ደም ባንክ አገልግሎት አስታውቋል።

የደም ማሰባሰቡ እንደ ሀገር ሲከናወን የቆየ ሲሆን፤ በሩብ ዓመቱ የተሰበሰው በአንጻሩ ካለፈው የተሻለ መሆኑን የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ታዬ ለአሐዱ ተናግረዋል።

እቅዱን ሙሉ ለሙሉ ለማሳካት የደም ለጋሽ በጎ ፈቃደኞች በሚፈለገው ልክ አለመሳተፍ፣ በአንዳንድ የጸጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ላይ ለመሰብሰብ አዳጋች መሆን እንዲሁም በበዓላት ወቅት ደም የመለገስ ሂደቱ አነስተኛ መሆንና መሰል ተግዳሮቶች እንዳጋጠሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል።

ለቀጣይ ክፍተቶችን በማረም የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ ተቋሙ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ኅብረተሰቡም በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አደባባዮች በሚገኙ ማዕከላት፣ በትምህርት ቤቶች፣ ቀይ መስቀል ግቢና በሁሉም የደም ባንክ መስሪያ ቤቶች ደም በበጎ ፈቃደኝነት መለገስ እንደሚችል አቶ ሀብታሙ አመላክተዋል።

በአለምነው ሹሙ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 12:43


የ12 ዓመት ታዳጊን ጫካ ውስጥ በማገት 500 ሺሕ ብር የጠየቁ ግለሰቦች እጅ ከፈንጅ መያዛቸው ተገለጸ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የ12 ዓመት ታዳጊን ጫካ ውስጥ በማገት 500 ሺሕ ብር የጠየቁ ግለሰቦች እጅ ከፈንጅ ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ ፖሊስ አስታውቋል።

በአዊ ብሔ/አስ/በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ የቻጃ ክብርታ ቀበሌ ነዋሪ የሆነ ወጣት ጥሩነህ ይግዛውና የጓንጓ ወረዳ ነዋሪ ወጣት ግዛቸው ወርቅነህ የተባሉ ግለሰቦች በቻግኒ ከተማ የ05 ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን የ12 ዓመት ህፃን ታጁ የሱፍን ጥቅምት 04/2017 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00  በባጃጅ በመውሰድ መሰወራቸው ተገልጿል።

ከዛም በማስከተል ወደ ታጋች ቤተሰብ ስልክ በመደወል 500 ሺሕ ብር እንዲከፍሉ ቢጠይቁም፤ የታጋች ቤተሰብ ከሀያ ሺሕ ብር በላይ የመክፈል አቅም  እንደሌላቸው ይገልጻሉ።

በዚህም ምክንያት አጋቾቹ ታዳጊውን በጓንጓ ወረዳ  ሰሜን ደገራ በተባለው ጫካ ውስጥ ለ8 ቀናት እንዲቆይ ማድረጋቸውን፤ የአየሁ ጓ/ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የወንጀል ምርማራ ክፍል ኃላፊ ዋና ሳጅን አዳነ ጥላሁን ተናግረዋል።

"አጋቾቹ  ታጋቹን ሕፃን ከ8 ቀናት የጫካ ቆይታ በኋላ ከጥቅምት 11_15/2017 ዓ.ም ድርስ በአየሁ ጓ/ወረዳ በቻጃ ክብርታ ቀበሌ ከጥሩነህ ይግዛው ቤተሰብ ጋር እንዲቆይ አድርገዋል" ሲሉ ያብራሩት የምርመራ ክፍል ኃላፊው፤ ማህበረሰቡ ባደረሰው ጥቆማና  የወረዳው ፖሊስ ባደረገው ክትትል ጥቅምት 15/2017 ዓ.ም በቦታው ድርስ በመሄድ እጅ ከፈንጅ  በመያዝ በወረዳው ፖሊስ ፅ/ቤት ምርመራ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል ።

"የድርጊቱ ፈፃሚዎች ለገንዘብ ሲሉ ድርጊት መፈፃማቸውን አምነዋል" ያሉት ዋና ሳጅን አዳነ፤ በዚህ ድርጊት የተሳተፉ ሌሎች ተባባሪ አካላትንም በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ እየሠሩ መሆኑን አብራርተዋል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 12:26


ባለሐብቶች ከገበሬዎች የሚያስመርቱት የእርሻ ምርት በገቡት ውል መሰረት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ተጠየቀ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በቅርቡ የተሻሻለው በኢንቨስተሮችና ገበሬዎች መካከል የውል እርሻ ምርት መመርያ ተፈፃሚ እንዲሆን በብርቱ እየሰራበት እንደሚገኝ ግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ መመርያውን ያሻሻለው በኢንቨስተሮችና በገበሬዎች መካከል የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን በዘላቂነት ለመፍታት በማለም መሆኑን ገልጿል።

በግብርና ሚንስቴር የእንስሳትና አሳ ሀብት ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ፅጌሬዳ ፍቃዱ የገበሬን እርሻ በውል የሚያስመርቱ ባለሐብቶች በኩል የሚስተዋለውን ችግር ለመቅረፍ ሲባል፤ አንዳንድ ሕጎች እንዲሻሻሉ መደረጋቸውን ለአሐዱ ተናግረዋል።

ሚኒስቴሩ የውል እርሻ ወይንም ኮንትራት ፋርሚንግ መመርያ አውጥቶ ተግባራዊ ሲያደርግ የቆየ ቢሆንም፤ በሕጉ ላይ መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች በመኖራቸው እንዲሻሻል መደረጉንም ገልጸዋል።

ዘርፉ በርከት ያሉ ቅሬታዎች ሲነሱበት የቆየ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም ምክንያት ማሻሻያ ማድረግ ማስፈለጉን ተናግረዋል።

የተሻሻለው ሕግ በዘርፉ የሚሳተፉ ባለሐብቶች እንዲሳተፉበት የሚያበረታታ መሆኑን የገለጹት ኃላፊዋ፤ ኢንቨስተሮችን ለመሳብ መንግሥት ጥረት እያደረገ እንደሚገኝም ለአሐዱ አስረድተዋል።

ሕጉ የውል እርሻ የሚል ስያሜ ተሰጥቶች ከዓመታት በፊት ተግባራዊ ቢደረግም የታለመለትን ያህል እንዳልተፈጸመ ተነግሯል። በዚህ የተነሳም ማሻሻያ አስፈልጓል ተብሏል።

በአማኑኤል ክንደያ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 11:24


#አሐዱ_ትንታኔ

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/Xo8iHCyL6cY?si=7rX0zPZUPWgw2CAR

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 11:00


በሐሰተኛ ሰነድ የሙያ ፈቃድ ዕድሳት የሚጠይቁ ባለሙያዎች መበራከታቸው ተገለጸ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) ሐሰተኛ ሰነድ በማቅረብ የሙያ ፈቃድ ዕድሳት የሚጠይቁ ባለሙያዎች ከጊዜ ወደጊዜ እየተበራከቱ መምጣታቸውን የአዲስ አበባ አስተዳደር የምግብና መድሐኒት ባለስልጣን አስታውቋል።

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች እና ተቋማት የፍቃድ ዕድሳት በመድረግ ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።

በከተማዋ የምግብና መድሐኒት ባለስልጣን የጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ብቃት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ታደሰ ወርዶፋ፤ ባለሙያዎች የሙያ ፍቃዳቸውን ዕድሳት ከማድረጋቸው በፊት እንዲሁም በሙያ ማህበራት አቅም ማጎልበቻ ሥልጣናን ሳያጠናቅቁ ሐሰተኛ መረጃዎችን ከየማህበራቸው በመውስድ ወደ ተቋሙ እንደሚመጡ ገልጸዋል።

እስካሁን ባለው ሂደት በ30 ባለሙያዎች ላይ እርምጃ መወሰዱን አንስተው፤ ይህ ሐሰተኛ ሰነድ የማቅረብ ሁኔታ በቁጥጥር ሂደቱ ላይ ተግዳሮት መሆኑንም ነግረውናል።

ሀላፊው አክለውም፤ ባለሙያዎች የፍቃድ ዕድሳት አድርገው የህብረተሰብ ሕይወት ላይ ስለሚሰሩ ስልጠናው አጠናቅቀው የዕውቅና ሰርተፍኬት መቀበል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

በመሆኑም ማህበራቱ ይህንን ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ስልጠናውን መስጠት እንዳለባቸው ጠቁመው፤ "ከጤና ሚኒስትር የሚላክ መረጃን ታሳቢ በማድረግ በተያዘው የጥቅምት ወር ላይ ሙሉ በሙሉ የማጣራት ሥራዎች ይከናወናሉ" ብለዋል።

ባለስልጣኑ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ዕድሳት ያላደረጉ የጤና ባለሙያዎችን ከህዳር 1 ጀምሮ የጤና ሚኒስተር ባወጣው መመሪያ መሰረት በቅጣት እንደሚስተናገዱ ማስታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።

በወልደሀዋርያት ዘነበ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

26 Oct, 08:51


"ህወሓት ከሦስት ወራት በኃላ ጉባኤ አዘጋጅቶ እንዲጠራን እንጠብቃለን" ምርጫ ቦርድ

ጥቅምት 16/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 3/2016 ዓ.ም. በቁጥር አ1162/11/15180 ለህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በጻፈው ደብዳቤ ፖርቲው በልዩ ሁኔታ በመመዝገብ የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀትም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም ሰርተፍኬቱ ከሰጠበት ቀን ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ በቀጣይ ሦስት ወራት ለጉባኤ እንዲጠሩን እንጠብቃለን ሲሉ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዉብሸት አየለ ለአሐዱ ተናግረዋል።

ሰርተፍኬቱ ሁለት መሰረታዊ ሃላፊነት ህወሓት ላይ ይጥላል ያሉት አቶ ውብሸት፤ የመጀመሪያው በ6 ወራት ውስጥ ጉባኤ እንዲያደርጉ መሆኑን ለአሐዱ ተናግረዋል። ጉባኤ ከማድረጋቸው ቀደም ብሎ ከ21 ቀን በፊት ለቦርዱ ማሳወቅም ይገባቸው ነበር ብለዋል።

ጉባኤ አድርገው አመራሮቻቸውን የምርጫ ቦርድ ታዛቢዎች ባሉበት መመርጥ ይጠበቅባቸው ነበር ሲሉም ነግረውናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ጠቅላላ ጉባዔውን ሊያደርግ መሆኑን በመገናኛ ብዙኃን መነገሩን ተከትሎ፤ ቦርዱ ለፓርቲው የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ጽፎ እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ህወሓት የቦርዱን ማሳሰቢያ ወደ ጎን በመተው ጉባኤውን ካደረገ፣ ለጉባኤው እና በጉባኤ ለሚተላለፉ ውሳኔዎች እውቅና እንደማይሰጥ ቦርዱ አሳስቦ ነበር፡፡

ነገር ግን ህወሓት የምርጫ ቦርድን ማሳሰቢያ ወደ ጎን በመተው 14ኛ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዷል፡፡

ከዚህም ጉባዔው ማብቂያ ላይ የድርጅቱን ምክትል ሊቀመንበር እና የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ 17 የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ከስልጣን ማንሳቱን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

አሁን ላይ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ዉብሸት፤ "ህወሓት የዕውቅና ሰርተፍኬቱን ካገኘበት ቀን ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ በቀጣይ ሦስት ወራት ውስጥ አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቶ ለጉባኤ እንዲጠራን እንጠብቃለን" ሲሉ ነው የተናገሩት፡፡

በአቤል ደጀኔ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 15:10


#አሐዱ_ትንታኔ

ትንታኔውን ለመከታተል ተከታዩን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://youtu.be/kJ8Lz_vtwKQ?si=t3RQ-baX-WkE40cH

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 14:51


ከሞሪንጋ ወይም ሽፈራው ተክል ዘይት ማምመረት የሚያስችል ፋብሪካ ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተገለጸ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርባ ምንጭ ከተማ ዘይሴ ቀበሌ፤ ከሞሪንጋ ወይም ሽፈራው ተክል ዘይት ማምመረት የሚያስችል ፋብሪካ ሥራ ሊጀምር መሆኑ ተገልጿል።

ፕሮጀክቱ በዋናነት ተግባራዊ የተደረገው እና ፋብሪካው የተገነባበት ተክሉ በስፋት የሚበቅልበት አርባ ምንጭ ከተማ ዘይሴ ቀበሌ ነው፡፡

የጣሊያን መንግሥት፣ የተባበሩት መንግሥታት  የኢንዲስትሪ ልማት ድርጅት እና የደቡብ ኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ልማት ኮርፖሬሽን ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ያስገነቡት መሆኑንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የኢንደስትሪ ልማት ድርጅት ተወካይ እና የፕሮጀክቱ ቴክኒካል አማካሪ ዶክተር ለምለም ሲሳይ፤ "የሞሪንጋ ተክል ወይም ሽፈራው በአካባቢው ማህበረሰብ "አለኮ" በመባል የሚታወቅ ቢሆንም ከምግብነት ባለፍ በሀገር አቀፍ እና በአለም ገበያ ላይ ተፈላጊ መሆኑ ባለመታወቁ ብዙ ትኩረት አልተሰጠው" ብለዋል፡፡

"የፕሮጀክቱ ዋና አላማ ማህበረሰቡ የሚያውቀውን ተክል በማምረት እና በማቀነባበር ወደ አለም ገበያ እንዲቀርብ ማድረግ ነው" ሲሉም አንስተዋል፡፡

ተክሉ ማህበረሰቡ ለዕለት ተእለት ከሚጠቀምበት ምግብ ባለፈ በፋብሪካ በማቀነባበር የሻይቅጠል ምርት፣ ዘይት እንዲሁም በኪኒኒ መልክ መጠቅም እንደሚቻል በውስጡም የተለያዩ ቫይታሚኖች እንዳሉት፤ በአርባ ምጭ ዩንቨርስቲ በተደረገው ጥናት እና ምርምር መረጋገጡን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

የሞሪንጋ ወይም የሽፈራው ተክልን በዘመናዊ መልኩ አቀነባብሮ እና አምርቶ ለገበያ ማቅረብ ለኢኮኖሚው ከሚያበረክተው አስተዋጾ በተጨማሪ የጤና ጠቀሜታ እንዳለው የተናገሩት ደግሞ፤ በተባበሩት መንግሥታት የኢንደስትሪ ልማት ድርጅት የምግብ ዋስትና እና የመሰረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ፌሪድ ኮንጎ ናቸው፡፡

ተክሉ በወቅቶች መፈራረቅ የማይደርቅ በመሆኑ የምግብ ዋስትናን በማረጋጋጥ አስተዋጾ እንዳለው አቶ ፌሪድ ገልጸዋል፡፡

"ፕሮጀክቱ በገጠር የሚገኙ ሴቶች ራሳቸውን ከማብቃት ባለፍ ቤተሰባቸውን በኢኮኖሚ እንዲደግፉ ያስችላቸዋል" ነው ያሉት፡፡

ሞሪንጋን ወይም ሽፈራውን ለምግብነት ከመጠቅም ባለፈ የተለያዩ የብስኩት አይነቶችን መስራት እንደሚቻልም አንስተው፤ "ከሌሎች ምግቦች ጋር በመቀላቀል ለተማሪዎች ምግባ ላይ መጠቀም ይቻላል" ሲሉም ለአሐዱ አስረድተዋል፡፡

መሠረተ ልማቶችን በማሟላት እና ፖሊሲ በማውጣት የሀገር ውስጥ ገበያ ትስስርን ከመፍጠር አንጻር የክልሉ መንግሥት የሚያደርገው ትብብርም የሚበረታታ መሆኑን ተናግረው፤ ፋብሪካው በቅርቡ ሥራ እንደሚጀምርም ጠቁመዋል፡፡

በፍቅርተ ቢተው

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 14:35


ከካማላ ሀሪስ በተሻለ የዶናልድ ትራንፕ መመረጥ ለአፍሪካና አፍሪካውያን የተሻለ ነው ተባለ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በመጪዉ ጥቅምት 26 ለሚደረገዉ ምርጫ በተለይ ለፕሬዝዳንትነት በሚወዳደሩት በቀድሞዉ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕና በምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሐሪስ መካከል ጠንካራ ፉክክር እየተደረገ ነው።

የምርጫዉ ዉጤት ዩናይትድ ስቴትስ እንደ አብዛኛዉ ዓለም ሁሉ ከአፍሪካ ጋር በሚኖራት ግንኙነት ላይ ተፅዕኖ እንደሚያሳርፍም በሰፊዉ ይታመናል።

ዶናልድ ትራንፕ ፕሬዝዳንት በነበሩበት ወቅት የአፍሪካ የመሠረተ ልማት አዉታር እንዲሻሻልና የአፍሪቃና የዩናይትድ ስቴትስ ፖለቲካዊ ግንኙነት እንዲዳብር አድርገዋል የሚሉት አለም አቀፍ ፖለቲካ ተንታኞች ናቸው።

በተለይ በጤና ጥበቃ ሁኔታዎች ላይ የተሻለ አበርክቶ የነበራቸው ትራንፕ በሌላዉም መስክ አፍሪቃን ረድተዋል የሚለው ጉዳይ የሳቸው መመረጥ ለአፍሪካና አፍሪካውያን መልካም ስለመሆኑ ይታመናል መባሉን የሮይተርስ ዘገባ አመላክቷል፡፡

አሁን ላይ ለኋይት ሀውስ የሚደረገው ውድድር የመጨረሻዎቹ ሳምንታት ላይ ሲሆን፤ እንደ አሪዞና እና ጆርጂያ ያሉ ቁልፍ ግዛቶችን ጨምሮ በተለያዩ ግዛቶች ላይ ቀደም ብሎ ድምጽ የመስጠት ሂደቱ ተጀምሯል።

ኹለቱ የከፍተኛ ፓርቲ እጩዎች፣ የዴሞክራቲክ ምክትል ፕሬዝዳንት ካማላ ሃሪስ እና የሪፐብሊካኑ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመዘዋወር ገንዘብ የማሰባሰብ እና መራጮችን የመቀስቀስ ሥራን በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡

ዶናልድ ትራምፕ ወደ ሥልጣን ይመለሳሉ ወይንስ፤ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዘዳንት ሊሆኑ የሚችሉት ካማላ ሃሪስን ይመረጣሉ የሚለው ብዙዎችን እያነጋገረ ይገኛል፡፡

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 13:51


በጋምቤላ ክልል ኮንዶም በውድ ዋጋ እየተሸጠ ነው በሚል የተሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነዉ ተባለ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በጋምቤላ ክልል የኮንዶም ስርጭት የለም እንዲሁም በውድ ዋጋ እየተሸጠ ነው በሚል የተሰራጨው መረጃ ከእውነት የራቀ ነዉ ሲል የክልሉ ጤና ቢሮ አስታውቋል፡፡

በጋምቤላ ክልል ኮንዶም ከመቶ ብር በላይ በሆነ ዋጋ እየተሸጠ እንደሚገኝና፤ በክልሉ ከፍተኛ የሆነ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት ስለመኖሩ ከዚህ በፊት መዘገቡ ይወሳል።

ከዚህ ጋር ተያይዞም የጤና ቢሮው ኃላፊ ዶክተር አቤል አሰፋ፤ በክልሉ የኮንዶም ስርጭት የለም፣ በከፍተኛ ዋጋ እየተሸጠ ነው ተብሎ የተሰራጨው መረጃ ሃሰተኛ ነው ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ኃላፊው አክለውም፤ በተለይም ኤች አይ ቪ ኤድስን ለመከላከል የሚያስችሉ ተግባራት በስፋት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸው፤ በዚህም በክልሉ የበሽታው ተጠቂ ቁጥር ከ3.69 ወደ 3.2 በመቶ ዝቅ ማለቱን ተናግረዋል፡፡

በዚህም መሰረት የክልሉ ጤና ቢሮ ኮንዶምን በነፃ እያሳራጨ እንደሚገኝ ጠቅሰው፤ ያልተረጋገጠ መረጃን የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል፡፡

በተጨማሪም ሌሎች አካላትም ለገበያ በሚቀርቡት ኮንዶም ላይ የዋጋ ንረት እንዲይኖር ቁጥጥር እንደሚያደርጉም ጠቁመዋል።

በፅዮን ይልማ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!

ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 12:44


20 ከመቶ የሚሆነዉ የኤሌክትሪክ ሀይል ለብክነት እንደሚዳረግ ተገለጸ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በኢትዮጵያ 20 ከመቶ የሚሆነዉ የኤሌክትሪክ ሀይል ለብክነት እንደሚዳረግ የኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሀይል አስታውቋል።

በተያዘው ሩብ ዓመት ከተመረተው 6 ሺሕ 4 መቶ 56 ጊጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሃይል ውስጥ 6 ሺሕ 4 የሚሆነው መሸጡን የተቋሙ የኮምኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ የሚመረተው የኤሌክትሪክ ሀይል እና ያሉት መሰረተ ልማቶች አለመጣጣም የኤሌክትሪክ ሀይል በሚፈለገው ልክ ለተጠቃሚዎች እንዳይደርስ ችግር መሆኑ በተደጋጋሚ የሚነሳ ጉዳይ ነው።

አሐዱም ይህን መነሻ በማድረግ ባለፉት ሦስት ወራት ምን ያክል ሀይል ተመርቶ ምን ያክሉስ ጥቅም ላይ ዋለ? በማለት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሀይል የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ጠይቋል፡፡

የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተሩ "ባለፈው ሩብ ዓመት አጠቃላይ የተመረተው የኤሌክትሪክ ሀይል 6ሺ 4መቶ 56 ጊጋ ዋት ነዉ" ያሉ ሲሆን፤ "ቀሪው 452 ኪጋ ዋት ተቋሙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚጠቀምበትን እና የባከነን ሃይልም አንድ ላይ የሚይዝ ነው" ሲሉ ገልጸዋል፡፡

እንደተቋም ይባክናል ተብሎ የሚታሰበዉ የሃይል መጠን 7 ከመቶ ያክል ነው ያሉት አቶ ሞገስ፤ እንደ ሀገር ያለው የብክነት መጠን 20 ከመቶ እንደሆነና "ይህ መጠን ከፍተኛ ነው ለማለት የአለማቀፍ ደረጃዎችን ማየት ያስፈልጋል" ሲሉም አክለዋል፡፡

በእመቤት ሲሳይ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡ https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 11:53


"አብያተ እምነት ተቋማት የሰማያዊ መንግሥት ተልዕኮ ማስፈጻሚያ ኤምባሲዎች በመሆናቸው ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል" እናት ፓርቲ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) እናት ፓርቲ አብያተ እምነት ተቋማት የሰማያዊ መንግሥት ተልዕኮ ማስፈጻሚያ ኤምባሲዎች በመሆናቸው ጥበቃ ሊደረግላቸው ይገባል ሲል፤ በወቅታዊ ጉዳዮች እና የኮሊደር ልማትን በተመለከተ በሰጠዉ መግለጫ አሳስቧል።

ፓርቲዉ በመግለጫው፤ "ከኮሪደር ልማት ፕሮጀክት ጋር ተያይዞ በአዲስ አበባ ከተማና ዙሪያዋ በሚገኙ ከተሞች የአምልኮ ሥፍራዎች ሕጋዊ ይዞታዎች ድንበር በማን አለብኝነት እየፈረሰ እንዳለ መረጃዉ ደርሶኛል" ብሏል።

የአብያተ እምነት ተቋማት ለሰው ልጅ አጠቃላይ መንፈሳዊና አእምሯዊ ልዕልና ያላቸው ሚና አይተኬ እንደሆነም ገልጿል።

"እየፈረሱ ካሉት በዋቢነት የሰበታ ጌቴሴማኒ ቤተደናግል ጠባባት የሴቶች ገዳም ይዞታ ከክብር በወረደ አኳኋን እንዲፈርስ የተደረገ ሲሆን፤ ከየካቲት አስራ ሁለት አደባባይ ከፍ ብሎ ያለውና ከአምስቱ ዓመት የፋሽስት ጣልያን ወረራ ወቅት ጋር ቀጥተኛ ተያያዥ ታሪክ ያለው የአገር ባለውለታው የምስካዬ ኅዙናን መድኃኔዓለም ገዳም ይዞታም ጠባብ የሆነውን ዐውደ ምሕረት የበለጠ በማጥበብ ከፊት ለፊቱ የገዳሙና የገዳሙ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ፈረሳ እንደሚከናወንባቸው ፓርቲያችን መረጃ ደርሶታል" ብሏል።

እነዚህን በዋቢነት ተጠቀሱ እንጂ ፈረሳው ያነጣጠረባቸው በአዲስ አበባ ከተማና አካባቢው የሚገኙ አብያተ እምነት ቁጥር ብዙ እንደሆነ መረዳቱን ፓርቲው ገልጿል።

ስለሆነም "መንግሥት ከዚህ ነባር ሃይማኖት አካሄድ እንዲታቀብና የአብያተ እምነት ቅጥሮችን ማፍረሱን በአፋጣኝ እንዲያቆም በጽኑ እናሳስባለን" ሲልም በመግለጫው አስታዉቋል፡፡

በፅዮን ይልማ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 10:07


ፓስፖርት ለማውጣት "የአምስት ሺሕ ብር ሲስተም የለም" እየተባልን ነው ሲሉ ተገልጋዮች ቅሬታ አቀረቡ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 20 ሺሕ እና 25 ሺሕ ብር ከሚያስከፍሉት የአስቸኳይ አገልግሎቶች በስተቀር በመደበኛ ከፍያ እያስተናገደን አይደለም ሲሉ ተጋልጋዮች ቅሬታቸውን ለአሐዱ አቅርበዋል፡፡

ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ "5 ሺሕ ብር ከፍለን በመደበኛው ጊዜ ፓስፖርታችንን መውሰድ አልቻልንም" ያሉ ሲሆን፤ "ለዚህም የሚሰጠን ምክንያት ‹‹ሲስተሙ አይሰራም›› የሚል ነው" ብለዋል፡፡

አክለውም "የፓስፖርት አገልግሎት ክፍያውን መምረጥ ያለበት ተጠቃሚው ነው፡፡" ያሉ ሲሆን፤ "በ2 ቀን እንዲደርስላችሁ 25 ሺሕ ብር በ10 ቀን እንዲደርስላችሁ ደግሞ 20 ሺሕ ብር ክፈሉ መባላችን ትክክል አይደለም፡፡ በመረጥነው ክፍያ ልንስተናገድ ይገባል" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ አዲስ የማክሮ ኢኮኖሚይ ማሻሻ ማድረጓን ተከትሎ፤ የክፍያ መሻሻሎች ካደረጉ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች መካከል አንዱ፤ የኢትዮጵያ ኤምግሬሽን የዜግነት አገልግሎት መሆኑ ይታወቃል።

የኢምግሬሽን የዜግነት አገልግሎት ለዜጎች  ፓስፖርት ለመስጠት ሲል የክፍያ እና የጊዜ ቀነ ገደብም አስቀምጧል፡፡

ዜጎች በሁለት ወራት ውስጥ ፓስፖርት ለማግኘት ዝቅተኛው ክፍያ አምስት ሺሕ ብር መሆኑን አገልግሎቱ  በወቅቱ ያሳወቀ ቢሆንም፤ ተገልጋዮች "አምስት ሺሕ ብር ከፍሎ  ፓስፖርት የማግኘት ሲስተም ለጊዜው የለም እየተባለን እየተመለስን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

ሌላኛው ሥማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ተገልጋይ በበኩላቸው፤ "የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ወደ ኢምግሬሽን የዜግነት አገልግሎት የሄድን ቢሆንም፤ ከመጉላለት በዘለለ በፓስፖርት ወረፋ ወቅት ያለው ወከባ እና ግርግር ለደህንነታችን አስግቶናል" ብለዋል፡፡

አሐዱ "ለአስቸኳይ ከፍተኛ ከፋዮች የሚሰራው ሲስተም ለዝቅተኛ ከፋዮች የማይሰራበት ምክንያት ግልጽ አይደለም" የሚለውን የተገልጋዮች ቅሬታ በመያዝ ከኢትዮጵያ የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ምላሽ ለማግኘት በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ፤ የአገልግሎቱ የሥራ ሃላፊዎች ስልክ ባለማንሳታቸው እንዲሁም አንስተው "ጉዳዩ አይመለከተንም" በማለታቸው ምክንያት ምላሹን ማካተት አልቻለም፡፡

ተቋሙ ለቅሬታው ምላሽ በሚሰጥበት ጊዜ ግን ምላሹን ይዘን እንቀርባለን፡፡

በደረጄ መንግሥቱ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 09:11


የእንስሳት ክትባት የሚያመርቱ አራት የውጭ አገር ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ፋብሪካቸውን ሊተክሉ መሆኑን ተሰማ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በቅርቡ የእንስሳት ክትባት የሚያመርቱ አራት የውጭ አገር ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ፋብሪካቸውን ሊተክሉ መሆኑን የግብርና ባለስልጣን አስታውቋል።

በኢትዮጵያ የሚስተዋለውን የእንስሳት ክትባት ችግር የተነሳ የእንስሳት ጤና አጠባበቅ ላይ ክፍተት ሲስተዋል መቆየቱን ባለስልጣኑ ተናግሯል።

ወደ ኢትዮጵያ ገብተው ክትባት ለማምረት የተስማሙት ኩባንያዎች፤ የችግሩን ስፋት ያጠቡታል የሚል እምነት እንዳለ በግብር ባለስልጣን የእንስሳት መድሀኒት ቁጥጥር ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ሰለሞን ከበደ ለአሐዱ ተናግረዋል።

ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ ደረጃ የእንስሳት ክትባት የሚያመርት ድርጅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእንሰሳት ጤና ጥበቃ ኢንሰቲትዩት ብቻ እንደነበር የገለጹት ኃላፊው፤ "የውጭ ኩባንያዎችን ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ መፈቀዱ ክፍተቱን መድፈን ያስችላል" ብለዋል።

ወደ ሀገር ይገባሉ የተባሉት ክትባት አምራች ኩባንያዎች የማምረተ አቅምና የጥራት ደረጃቸውን በተመለከተ ሰፊ ግምገማ ሲደረግለት መቆየቱን ዶክተር ሰለሞን አስታውሰዋል።

መንግሥት የያዘው የእንስሳት ጤና ጥበቃ እንቅስቃሴ አካል መሆኑን ኃላፊው ጨምረው ለአሐዱ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ በብቸኝነት የእንስሳት ክትባት በማምረት የሚታወቀው የመንግሥት የልማት ድርጅት የሆነው ብሔራዊ የእንሰሳት ጤና ጥበቃ ኢንሰቲትዩት ሲሆን፤ የተቋቋመው በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ እንደነበር ይታወቃል።

በርካታ የውጭ ምንዛሪ ከሚጠይቁ የግብርና ምርቶች መካከል አንዱ የእንስሳት ክትባት ተጠቃሽ መሆኑን በግብርና ባለስልጣን የእንስሳት መድኃኒት ቁጥጥር ኃላፊው ከዶክተር ሰለሞን ለማወቅና ችለናል።

በአማኑኤል ክንደያ

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ

AHADU RADIO FM 94.3

25 Oct, 09:01


ርዕሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ ለ34 የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጡ

ጥቅምት 15/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ፤ ለ34 የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ሹመት ሰጥተዋል።

በዚህ መሠረት፦

1. አማኑኤል ፈረደ አያሌው (ዶ.ር)  በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአብክመ ርእሰ መሥተዳደር ልዩ አማካሪ

2. መስፍን አበጀ ተፈራ (ዶ.ር) - በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርእሰ መሥተዳደሩ የዴሞክራሲ ባህል ግንባታ ዘርፍ አማካሪ

3. ወ/ሮ መሰሉ ብርሃኑ ካሳው  -   የአብክመ ቆላና መስኖ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

4. አቶ ደረጀ ማንደፍሮ ዳመነ -  የአብክመ ግብርና ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

5. አቶ ፈንታሁን ስጦታው ፈለቀ  - በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአብክመ ግብርና ጥራትና ደህንነት ባለስልጣን ኃላፊ

6. አቶ ደምስ እንድሪስ ይማም - የአብክመ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

7. አቶ ጥላሁን ፈንታው ተሾመ -  የአብክመ ፕላን ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

8. ወ/ሮ ትብለጥ መንገሻ አማረ -  የአብክመ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

9. አቶ ሙሉነህ ዘበነ ሳህሌ - የአብክመ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

10. ወ/ሮ አትክልት አሳቤ ታምሩ - የአብክመ ንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

11. አቶ ዘላለም አረጋ መኮነን - የአብክመ ወጣትና ስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

12. ወ/ሮ ሃናን ይመር አሊ - በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአብክመ ሴ/ህ/ማ/ጉ ቢሮ ረዳት አማካሪ

13. አቶ አባይነህ ጌጡ ያሬድ  - በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የህዳሴ ግድብ ማስተባባሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ

14. አቶ አታላይ ክብረት ማሩ - በኤጀንሲ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት የክልል ተቋማት ክትትል አማካሪ

15. አቶ ይርጋ አላምነህ ወርቅነህ - በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የርዕሰ መስተዳደር ጽ/ቤት የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ረዳት አማካሪ

16. ወ/ሮ ውዴ እውነቱ አዳምነው - በምክትል ኤጀንሲ ኃላፊ ደረጃ የካቢኔ ሴክረታሪያት ኃላፊ

17. አቶ ዳዊት አቡ አለሙ -  የጣና ሐይቅና ሌሎች ውሃ አካላት ጥበቃና ልማት ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ

18. አቶ ወርቁ ኃ/ማርያም ጌጡ - የአብክመ በየነ መንግስታት ግንኙነት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ

19. አቶ ዮናስ ይትባረክ አበበ - በምክትል ቢሮ ኃላፊ ደረጃ የአማራ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ልማትና ማስፋፊያ ድርጅት ስራ አስኪያጅ

20. አቶ ፋሲል ሰንደቁ አደመ - በም/አስተዳዳሪ ማዕረግ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር የህዝብ ግንኙነት እና  አደረጃጀት ዋና አማካሪ

21. አቶ ሙሉጌታ ንጋቱ ለገሰ  -  የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር ዉሃና ኢነርጂ መምሪያ ኃላፊ

22.አቶ ስጦታው ሰጤ ነጋሽ - የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አስተዳደር ገቢዎች መምሪያ ኃላፊ

23. ወ/ሮ ካሳየ ስመኝ ዋሴ - የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ደንና አካባቢ ጥበቃ ተጠሪ ጽ/ቤት ኃላፊ

24. አቶ ሙሉጌታ አለም አድገህ   - የምዕ/ጎጃም ዞን አስተዳደር ሰላም እና ፀጥታ መምሪያ ኃላፊ

25. አቶ አግማስ  አንተነህ ውቤ - የምዕ/ጎጃም ዞን አስተዳደር  ምክትል አስተዳዳሪና ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት መምሪያ ኃላፊ

26. አቶ  መንግስቱ  አየለ ደምለዉ - የሰሜን ጎጃም ዞን አስተዳደር  መንገድና ትራንስፖርት መምሪያ ኃላፊ

27. አቶ  ስጦታው መርሻ አጆነህ - የሰሜን ጎጃም ዞን አስተዳደር  ማዕድን መምሪያ ኃላፊ

28. አቶ ንብረት አበጀ አለሙ  -  የሰሜን ጎጃም ዞን አስተዳደር  ስራና ስልጠና መምሪያ ኃላፊ

29. አቶ ዘውዱ  ላቀው  ሞገስ -  በም/አስተዳደሪ ማዕረግ ለሰሜን ጎጃም ዞን አስተዳደር ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር አማካሪ

30. ወ/ሮ የሽወርቅ ድረስ ተሰማ  - የሰሜን ጎጃም ዞን አስተዳደር  ትምህርት መምሪያ ምክትል ኃላፊ

31. ወ/ሮ ፀሐይነሽ ተፈራ በላይነህ -  የሰሜን ጎጃም ዞን አስተዳደር ገንዘብና ኢኮኖሚ መምሪያ ምክትል ኃላፊ 

32. አቶ ዘነበ ሀይሉ ተ/ፃዲቅ  -  የሰሜን ሽዋ ዞን አስተዳደር ህብረት ስራ ማህበራት ተጠሪ ጽ/ቤት ኃላፊ

33. ወ/ሮ ተዋባች ጌታቸው ዘዉዴ - የሰሜን ሽዋ ዞን አስተዳደር ዞን ባህል ቱሪዝም መምሪያ ኃላፊ

34. አቶ ዋሲሁን ብርሀኑ ሰብስቤ  - የሰሜን ሽዋ ዞን አስተዳደር ዞን ትምህርት መምሪያ ምክትል ኃላፊ በመሆን መሾማቸውን አሚኮ ዘግቧል፡፡

ተሿሚዎች በተለያዩ የመንግሥት የሥራ ኃላፊነቶች የሠሩ ሲሆን የላቀ ዕውቀት፣ ብቃት፣ ቁርጠኝነት እና ታታሪነት ያላቸው ስለመሆኑም ተገልጿል።

ትክክለኛዎቹን የአሐዱ ራዲዮ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ!
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ድረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ቲክቶክ ፡- www.tiktok.com/@ahadutv.official
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ