Addis Admass @adissadmas Channel on Telegram

Addis Admass

@adissadmas


የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
=====
አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx
ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv

የእርስዎና የቤተሰብዎ

Addis Admass (Amharic)

አስፈላጊ መግለጫnn"Addis Admass" የማኅበራዊ ትስስር ገጾች እና የእርስዎና የቤተሰብዎ አዲስ አድማስ የትምህርት ፕሪንትስ ነው። የሚሆንን በባሕርዳር ከተማ ተማ-ለደቡብ ሲሆን የትምህርት ፕሪንትሲ፣ በሚል ርዝመት ግሩም ይሏታል።nnበአድማሱ ወቅታዊ መንገድ እንደሚመኝ ተቆሞታል። አይሰሩም። አዲስ አድማስ በጊዜው እንዴት እንዳለ በርካታ ተሳሳቢ ሲሆን አለመብላት ይፈቅዳሉ።nn"Addis Admass" ከዚህ በፊት አካባቢዎቹን እና ትልቁ ህዝቦችን ለማግኘት የጅምላ ፕሪንትስ ይዘው የሚያሳርፉን ሰዎችን በእንግዳ ከተማው ደንበኞች አምልክት ያስቀናሉ።nnከዚህ በመጠን ለመረጃና ምልክት ቡድኖቹዎን ሊተግቧ እንችላለን። የአዲስ አድማስ መረጃ እና በታች በመጠቀም በፍጥነት ብዙ ውህቻ እንችላለን።nnእባኮትን የሚያጋጥሙን እና መረጃዎቹን ወደ በፊት ሥራ ለመስራት ኢሜል እንልናለን: [email protected]እናመሰግናለን እና ከግንቦት፤ ከማታሳውቅ፤ አካባቢዎቹን ስነስርኡል ይቀየሩ። በምርጫው ተመልከቱ።

Addis Admass

18 Feb, 21:20


11ኛ ቀኑን በያዘው የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ መርኃ ግብር እስካሁን 400 ሚሊዮን ብር መሰብሰብ ተችሏል።

Addis Admass

18 Feb, 20:57


ሜታ ኩባንያ 50 ሺህ ኪ.ሜ የሚረዝም የባህር ውስጥ ኬብል ሊዘረጋ ነው
***
ዋተርዎርዝ የተሰኘው ይህ ግዙፍ የቴክኖሎጂ ፕሮጀክት አሜሪካን፣ ህንድን፣ ደቡብ አፍሪካን፣ ብራዚልን የሚያካልል ሲሆን ሲጠናቀቅ በዓለም ረጅሙ የውሀ ውስጥ ኬብል ፕሮጀክት እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡
አዲሱ የኬብል ፕሮጀክት አምስት አህጉራትን በቀጥታ የሚያስተሳስር ሲሆን ፕሮጀክቱ የሰው ሰራሽ አስተዉሎት ቴክኖሎጂዎችን የሚጠቅም ነው ተብሎለታል፡፡
ፕሮጀክቱ ኢኮኖሚያዊ ትብብርን እና የቴክኖሎጂ እድገትን የሚያፋጥን ነው ሲል የገለፀው ኩባንያው፤ የሚጠቀመው 24 ፋይበር ጥንድ ሲስተም ረጅሙ የባህር ውስጥ ሲስተም እንደሚሆንና ይህም ከፍተኛ አቅም እንደሚጨምር ገልጿል፡፡
በባህር ውስጥ የሚዘረጉ የተለያዩ ኬብሎች ዲጂታል አገልግሎቶችን እና መረጃዎችን ለማስተላለፍ ተመራጭ አንደሆኑ ይነገራል፡፡
95 በመቶ የሚሆነው የአለም የኢንተርኔት መስመር የሚተላለፈው በባህር ስር በሚዘረጉ ኬብሎች መሆኑም ተጠቁሟል፡፡

Addis Admass

18 Feb, 20:48


ሽሙንሙን ሽሙንሙን
የማትጠገቢ


አንቺ ቆንጆ
የቆንጆ ቋት
የልብ ጌጥ
የዓይን መብራት።

አንቺ ገንቦ
የፅጌ ማፍያ፣
ቢራቢሮ
ዓይን ማረፊያ።

አንቺ ንጋት፣
ገላጭ
ብራ

አንቺ ኮከብ
ፀሐይ
ጮራ

አንቺ ፀዳል
የውበት ኩል
የት እንጣሽ
በዬት በኩል!?

ወቅትም አንቺ
በልግ
በጋ

ሀገር አንቺ
ቆላ
ደጋ

አንቺው መዓልት
ምሽት
ንጋት

አንቺው ዕድሜ
ማታና
ጧት።

ቴዎድሮስ ካሳ
(የዱር አበባ)
ጥቅምት 2017 ዓ.ም

Addis Admass

18 Feb, 20:47


የኑሮ ሽንቁር
**

ታምሜ አላውቅም ነበረ ። ይኸው ዛሬ ሆስፒታል ገብቼ ተኝቻለሁ። አጠገቤ ጉሉኮስ ያለበት ላስቲክ በረጅም የብረት ዘንግ ላይ ተንጠልጥሏል ። ጠብ ጠብ እያለ በአይበሉባዬ ላይ በተሰካው መርፌ አድርጎ ወደ ሰውነቴ ይፈሳል ።

አጠገቤ ስጋዋ ከላይዋ ላይ ያለቀ አሮጊት ፈረንጅ ተኝታለች ። አንዳንዴ ታቃስትና ገልበጥ ብላ ታንኮራፋለች ። ነርሶቹ መጥተው ሲነኳት ትነጫነጫለች ። እነርሱም ብዙ አያስቸግሯትም ። በራፍ ላይ ቆመው ብዙ ጥንቃቄ ሳያደርጉ ይንሾካሾካሉ። ግን ለእኔ ግልፅ ሆኖ ይሰማኛል ።

"እዚህ ቦታው ይፈለጋል ። መሞቷ ላልቀረ ሆስፒስ ቢወስዷት ይሻላል" ትላለች አንደኛዋ ። ( ሆስፒስ በቅርብ ይሞታሉ ተብለው የሚጠበቁ ሰዎች የሚቀመጡበት ቦታ ነው)

ሌላኛዋ ደግሞ " እዚያም ሌሎች ሞታቸውን የሚጠብቁ አሉ ፣ ቦታው ሞልቷል" ትላለች ።

አሮጊቷ የሰማች ይመስል ተገላበጠች ። እኔን ፍርሃት ያዘኝ ። ትኩር ብዬ እየተመለከትኩ አንዴ ትንፋሿን ፣ ሌላ ጊዜ ደግሞ የተገጠመላትን መቆጣጠሪያ እመለከታለሁ። ጥቁር መስመር በተነፈሰች ቁጥር አብሮ የሚዘል ምልክት ይታያል። የልቧ ትርታና የደም ግፊቷ 100/65 አብሮ ይታያል ።

እሷን ትቼ የእኔን የጉሉኮስ ጠብታ ማየት ጀመርኩ ። በዚች ጠብታ ይሄ ሁሉ መቼ ነው የሚያልቀው ብዬ አሰብኩ። ጉሉኮስ በሕይወቴ ሁለተኛ ጊዜ ሲደረግልኝ ነው ። ልጄን የወለድኩ ጊዜም ተደርጎልኝ ነበረ ። ያ አስከፊ ዘመን ፊቴ ላይ መጥቶ ተጋረጠ ። እንኳን ያኔ አላስወጣሁት አሁን ማን ከጎኔ ይሆን ነበር ብዬ ፈገግ አልኩ ።

አሮጊቷ ማንም የሚጠይቃት የለም ። ልጆች አይኖሯት ይሆናል ብዬ አሰብኩ። ለስራ ደፋ ቀና ስትል ጊዜ አልፎባት ይሆን ? ወይስ የጎረቤትን ሃሜት ፈርታ አስወጥታው ? ደግሞ ጀርመኖች ማንን ፈርተው ።

እንደገና ስለራሴ ማሰብ ጀመርኩ። ያፌትዬን ያረገዝኩት ከፍቅረኛዬ ነበር ። ሳላገባ አርግዤ ዲቃላ ነው ያመጣሁት ። እንደሱ ሲሆን ደግሞ ሁለት እርግዝና ነው ። ሰው ማርገዜን እንዳያውቅ መጨነቁ ራሱ መከራ ነው። አይ ያ ጊዜ ሲያስጠላ። የጓደኞቼ ወላጆች ልጆቻቸው ከእኔ ጋ እንዳይገጥሙ ከለከሉ። የሰፈር አሮጊት እንደ ድንገት ካዩኝ ግልምጫቸው ፣ አሽሙራቸው አይጣል።
እናቴ ብቻ ብቻዋን ከእኔ ጋ እንደተሰቃየች ። ያፌትዬ ግን እስከ ዕለተ ሞቷ ሲንከባከባት ነበረ ። " አንተ እኮ ለእኔ ነው የተወለድከው " ትለው ነበረ ። እሱ ለእሷ ያለውን ፍቅር ሳይ ይገርመኛል ። እንዲውም እኔን የቀረበኝ እሷ ከሞተች በኋላ ነው ።

አሮጊቷ እንደገና ማቃሰት ጀመረች ። እሷ ማቃሰት ስትጀምር የልብ ትርታዋን ከሚያሳየው መቆጣጠሪያ ሞኒተር ጋ ወደ ላይ የሚጨምር ምልክት አለ ። የሕመሟ መለኪያ ይመስላል ። እሱ ወደ ታች ሲወርድ እሷ መቃሰቷን አቁማ ማንኮራፋቷን ትቀጥላለች ።

እሷ መንኮራፋት ስትጀምር እኔ ጠብታዋን እያየሁ በሃሳብ እነጉዳለሁ። ያፌት እንደ ተወለደ ወደ ቤት አልሄድኩም ። አረገዘች በሚል በሰፈር ሞቆ የነበረው ወሬ ወለደች በሚለው እንደገና መጋሉ እስከሚበርድ አክስቴ ቤት ስድስት ወር ተቀመጥኩ። ሲበርድ ተመልሼ ወደ ቤት ገባሁ። ሁለት ዓመት ከተቀመጥኩ በኋላ ወንድሜ ወደ ጀርመን አመጣኝ ። ጀርመን ሦስት ዓመት ተቀምጬ ለእረፍት ስሄድ የሰፈሩ ሰው ሁሉ በደስታ ተቀበለኝ ። 'ያቺ ዲቃላ የወለደችው' መባሌ ቀርቶ ልዕልት ሆንኩ ። ጓደኞቼን ከእሷ እንዳትገጥሙ እንዳልተባሉ እነዚህ ገልቱዎችን ብትወስጂልንና እንዳንቺ ሰው ቢሆኑ ሲሉኝ ታዘብኳቸው ።

አሮጊቷ ተመልሳ ማቃሰት ጀመረች ። አሁን ግን ምልክቱ ወደ ታች አልወርድ አለ ። ዶክተሮቹ ለካስ እነርሱ ጋ መቆጣጠሪው አለ እየተሯሯጡ መጥተው መርፌ ወጓት ። ምልክቱ ወረድ አለ። መቃሰቷን ትታ ማንኮራፋቷን ቀጠለች ።

እኔም እንደ ገና የጉሉኮሱን ጠብታ ማየት ጀመርኩ ። ዓይኔ እየደከመ ሄደ ። ስነሳ የአሮጊቷ አልጋ አጠገቤ የለም ። ሞባይሌን አንስቼ ሰዓቱን አየሁ ። ለካ ሦስት ሰዓት ያህል ተኝቻለሁ። በዛ ሰዓት አሮጊቷ ሞታ ወደ ሬሳ ቤት ወስደዋታል ።

ጉሉኮሱ ግማሽ ያህል አልቋል ። በመኖርና ባለመኖር መካከል ያለው ልዩነት አንድ ትንሽ እንቅልፍ ነው ብዬ አሰብኩ። እንደገና ስለ ራሴ በሽታ አወጣ አወርድ ጀመር ።

ወደዚህ የመጣሁ በድንገት የመተንፈስ ችግር ገጥሞኝ ነው ። ደውዬ ሐኪሞቹን ስጠራቸው ወዲያው አፌ ላይ ኦክስጂን ገጥመው በአምቡላንስ እያጣደፉ አመጡኝ ። ጊዜም አልወሰዱ መርምረው ከሳምባዬ ውሃ መመጠጥ አለበት አሉ ። ውሃውን መጠው ካወጡ በኋላ ቀለል አለኝ ። ዶክተሩ መጥቶ "ውሃው ከየት እንደመጣ ማወቅ አለብን ። ትኩሳትሽም ሃይለኛ ስለሆነ መንስኤውን ማጣራት አስፈላጊ ነው ። ለዚህም ከተለያየ ቦታ ናሙና እንወስዳለን ። ካንሰር መሆኑንና አለመሆኑን እናጣራለን" አለኝ ።

በሩ ሲከፈት ቀና ብዬ ማየት ጀመርኩ ። የጠዋቷ ተረኛ ነርሷ ነበረች ቁርስ ይዛ የመጣችው ።

የናሙናውን ውጤቱን የማወቅ እንጂ ምንም የመብላት ፍላጎት የለኝም ። መጠበቅ እንዴት ያስጠላል ። ዶክተሩ መጥቶ "እናዝናለን ካንሰር ሆኖ አግኝተነዋል ። እንደ አሮጊቷ ያንቺም ቀን የተቆጠረ ነው ።" የሚል ይመስለኝና እደነግጣለሁ። አይ ሊሆን አይችልም የሚል ሃሳብ ይመጣብኛል ።

ቁርሱን ምንም ሳልቀምሰው ሌሎች መጥተው አንስተውት ሄዱ። ሃሳብ ይዞኝ ጭልጥ ብዬ ሄጄ ዶክተሩና ነርሷ እየሳቁ ወደእኔ ሲመጡ እን መባነን ነቃሁ።

" እንኳን ደስ አልዎት ። ካንሰር አይደለም ። አነስተኛ የሆነ ኢንፌክሽን ነው ። ለረጅም ጊዜ በሚወሰድ መድሃኒት ይጠፋል ። አይስጉ። "
አለኝ ዶክተሩ ።

እፎይታ ተሰማኝ ። ከሞት አፋፍ የተመለስኩ መሰለኝ ። ለካ ሕይወት እንዲህ አጭር ነች ። ጤንነት ከሌለ ደግሞ የበለጠ አስጠሊታ ነች ። ዘላለም የምንኖር እየመሰለን ብዙ እንተልማለን ። ግን ሕይወት በአቋራጭ ልታልቅ ትችላለች።

እነርሱ ሲወጡ ለያፌት ደወልኩለት ። ካንሰር አይደለም እንኳን ደስ አለን አልኩት ። በሰፊው ሲተነፍስ ይሰማኛል ። ከእኔ የባሰ የተጨነቀው እሱ ነበረ ።

ስልኩን ዘግቼ ጠብታ እያየሁ በሃሳብ ተዋጥኩ። እኔ ብሞት ያፌት ምን ይሆናል ? የሚለው ጥያቄ አሳሰበኝ ። ይኼ ሁሉ ለፍቼ አዲስ አበባ የሰራሁትን በሙሉ ማን ይሰጠዋል ። እህትና ወንድሞቼ አይንህ ላፈር እንደሚሉት አልጠራጠርም ። እንኳን እሱን በእናታችን ደሳሳ ቤት ሊጋደሉ አይደል የደረሱት ። በየትኛውስ አማርኛ ነው የሚከራከራቸው ። እሱም የፈለጉትን ያድርጉ ብሎ ዝም ነው የሚላቸው ። ለነገሩ "ማሚ ዝም ብለሽ ነው የምትለፊው እኔ እዛ ሃገር አልኖርም "ብሎ ቁርጤን ነግሮኛል።

አሁን ስድን ሄጄ ሁሉንም ሸጬ እዚሁ ጀርመን አንዲት አነስ ያለ ቤት እገዛለታለሁ ብዬ አሰብኮ ። ግን እኮ በአሁኑ ሰዓት ማን ይገዛኛል ?

ሳወጣ ሳወርድ ተጨነቅሁ መሰለኝ ሳሉ ጀመረኝ ። አሁን መጀመሪያ ጤንነቴ ብዬ ዩቱብ ላይ የሚያስደስት ነገር ፍለጋ ጀመርኩ።

ቤልጅግ ዓሊ

Addis Admass

18 Feb, 20:36


በርካታ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አገሮቻቸው ተመልሰዋል


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ የተካፈሉ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ቀዳሚ ምርጫ በመሆኑ ክብር እንደሚሰማው ገልጿል፡፡

38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ በስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ የበርካታ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በኢትዮጵያ አየር መንገድ አማካኝነት ወደ ሀገሮቻቸው መመለሳቸውን አየር መንገዱ አስታውቋል፡፡

በዚህም መሰረት የላይቤሪያ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ጆሴፍ ቦካይ፣ የብሩንዲ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ኤቭራስቴ ንዳሺሚዬ፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ፎውስቲን ታውዴራ፣ የሌሴቶ ጠ/ሚኒስትር ትሶኮአኔ ሳሙኤል፣ የካሜሩን ሪፐብሊክ ጠ/ሚኒስትር ጆሴፍ ንጎቴ እንዲሁም የጋምቢያ ሪፐብሊክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሙሃማድ ጃሎው አየር መንገዱን ምርጫቸው በማድረግ ወደ ሀገሮቻቸው ተመልሰዋል፡፡

"የአፍሪካ መሪዎች የኢትዮጵያ አየር መንገድን መርጠው ከእኛ ጋር ስለተጓዙ ክብር ይሰማናል" ያለው አየር መንገዱ፤ የሚሰጠውን የላቀ አገልግሎት በማጠናከር አፍሪካውያንን እርስበርስና ከተቀረው ዓለም ጋር የማገናኘት ተልዕኮውን በትጋት እንደሚወጣ አረጋግጧል፡፡

Addis Admass

18 Feb, 20:18


የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ 23ኛ የፋይናንስ ሚኒስትሮች ጉባኤ ተካሄደ

የአፍሪካ ቀንድ ኢኒሼቲቭ 23ኛው የፋይናንስ ሚኒስትሮች ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡

የወቅቱ የአፍሪካ ቀንድ ኢንሼቲቭ ሊቀ መንበርና የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሺዴ ጉባኤውን ሲከፍቱ፤ ከአምስት አመታት በፊት የተመሰረተው ኢንሼቲቩ በቀጣናው ያሉትን ሀገራት በኢኮኖሚ ትብብር የሚያስተሳስሩ የልማት ፕሮግራሞችን ለመተግበር የሚረዳ የሚኒስትሮች ማዕቀፍ ነው ብለዋል።

ኢኒሼቲቩ በልማት አጋሮች እንደሚደገፍም አቶ አህመድ ሺዴ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

በጉባኤው የልማት አጋሮች ቃል ከገቡት 15 ቢሊዮን ዶላር ውስጥ ግማሽ ያህሉ መገኘቱ የተጠቆመ ሲሆን፤ ኢንሼቲቩን ሲደግፉ የነበሩ ሦስት የልማት አጋሮችም ወደ አምስት ማደጋቸው ተመልክቷል፡፡

የኢንሼቲቩ የፕሮጀክት አፈጻጸም በአመዛኙ መልካም ቢሆንም፣ የአንድ አራተኛ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ግን አጥጋቢ በሚባል ደረጃ ላይ ባለመሆኑ ይህንኑ ማሻሻልና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ በጉባዔው ላይ ተገልጿል፡፡

በስብሰባው የቀጣናውን የልማት ትስስር ለማሳደግና ኢኒሼቲቩን ለማጠናከር የአየር ንብረት ለውጥ እቅዶችንና የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት የሚጠቅሙ አዳዲሰ የፋይናንስ አማራጮች የበለጠ በሚሰፉበት፣ ተጨማሪ ቀጣናዊ የፖሊሲ ማሻሻያዎች ተግባራዊ ስለሚደረጉበት እንዲሁም ከአጋሮች የተጠናከረ ድጋፍ በሚፈለግባቸው ዘርፎች ላይ አቅጣጫ መቀመጡም ተገልጿል፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ኢንሼቲቭ አባል ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ኬኒያ፣ ሶማሊያ፣ ጂቡቲ፣ ኤርትራ፣ ሱዳንና ደቡብ ሱዳን መሆናቸውን ከገንዘብ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
(ኢዜአ)

Addis Admass

18 Feb, 20:15


የቬትናም ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ

የቬትናም ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት እንዲሳተፉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ሚኒስትር ዴኤታው ጥሪውን ያቀረቡት የመጀመሪያው የኢትዮጵያና የሶሻሊስት ሪፐብሊክ ቬትናም የጋራ የፖለቲካ ምክክር በአዲስ አበባ በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡

በምክክሩ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ፤ ኢትዮጵያ እየተገበረች ያለው የኢኮኖሚ ማሻሻያ ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድል የፈጠረ በመሆኑ፣ የቬትናም ኩባንያዎች እንዲሳተፉ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢትዮጵያ ከቬትናም ፈጣን የኢንዱስትሪ እድገት ልምዶችን ለመቅሰም ፍላጎት እንዳላትም አምባሳደሩ ገልጸዋል።

የቬትናም የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚኒስትር ኑየን ሚን ሄን በበኩላቸው፤ ሀገራቸው ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኗን አስታውቀዋል፡፡

ሀገራቱ ከሁለትዮሽ ግንኙነት ባሻገር በባለ ብዙ-ወገን መድረክና በደቡብ ደቡብ ትብብር ግንኙነታቸውን የበለጠ ለማጠናከር ተስማምተዋል።

ኢትዮጵያ እና ቬትናም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት የጀመሩበትን 50ኛ ዓመት በቀጣይ ዓመት እንደሚያከብሩም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመልክቷል፡፡

Addis Admass

18 Feb, 20:14


በሃገራችንም በጥራት፣ በአቅርቦት፣ በአገልግሎትና ሌሎችም መገለጫዎች ተለይተው የሚታወቁና ከሃገር አልፎ በዓለም አቀፍ ገበያ ውስጥ የገቡ የምርቶችና የአገልግሎቶች ብራንዶች እንዳሉ የተጠቀሰ ሲሆን፤ ብራንድ ወይም ሎጎ ህጋዊ መሰረትን የሚይዘው በንግድ ምልክትነት ሲመዘገብ ነው ተብሏል፡፡ ይህም ህጋዊ ዕውቅናን የሚያስገኝና በብቸኝነት የመጠቀም መብትን የሚያጎናጽፍ ሲሆን፤ ተወዳዳሪነትና ኢኮኖሚያዊ ጥቅምንም ለማሳደግ እንደሚያስችል ተብራርቷል፡፡

በመርሃግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ እንዳሉ ሞሲሳ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉ ሲሆን፤ የማርኬቲንግና ብራንዲንግ ባለሙያው አቶ አስቻለው ታምሩ የተቋማት የብራንዲንግ ግንባታ በሚል ርዕስ በሃገራችን ስለብራንዲንግ ያለውን ግንዛቤና የተሰጠውን ትኩረት እንዲሁም የሌሎች ሃገራትን ተሞክሮ በጥልቀት ዳስሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን፣ የንግድ ምልክት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ትዕግስት ቦጋለ በበኩላቸው፤ የአዕምሯዊ ንብረት ምንነትና የንግድ ምልክት ጥበቃን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል - በምሳሌ አስደግፈው፡፡ የንግድ ምልክት ወኪል አቶ አባይ ፈለቀ ደግሞ የንግድ ምልክት ባለቤትነትንና ህጋዊ ሥርዓትን አስመልክቶ ግንዛቤ ማስጨበጪያ ለታዳሚው አቅርበዋል፡፡

በቀጣይ ይህን መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች ከኢትዮጵያ አእምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ጋር በመተባበር ለሌሎች ተቋማትና ድርጅቶች ለመስጠት ስምምነት መደረጉን የሙሌ ሚክስ መልቲሚዲያ ፕሮዳክሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉጌታ ጌቱ ገልፀዋል።

Addis Admass

18 Feb, 20:13


ለብራንድ አምባሳደሮችና ለብራንዲንግ ባለሙያዎች የግንዛቤ
ማስጨበጫ መርሃግብር ተካሄደ


የኢትዮጵያ አዕምሯዊ ንብረት ባለሥልጣን ከሙሌ ሚክስ መልቲ ሚዲያ ፕሮዳክሽን ጋር በመተባበር በዛሬው ዕለት የካቲት 11 ቀን 2017 ዓ.ም በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል ለብራንድ አምባሳደሮችና ለብራንዲንግ ባለሙያዎች “የንግድ ምልክት ምንነትና የብራንድ ጠቀሜታ” በሚል ርዕስ የግማሽ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃግብር ተካሄደ፡፡

በዚህ የውድድር ዓለም ምርቶችና አገልግሎቶች በውጤታማነት ለሸማቹ ማህበረሰብ ሊቀርቡ የሚችሉት መልካም ስምና ዝናን በያዙ ብራንዶች ወይም ንግድ ምልክቶች አማካኝነት ሲሆን፤ ብራንዲንግ ለብዙ ንግዶች ውጤታማነት ቁልፍ ሚና ይጫወታል ተብሏል፡፡ በስትራቴጂ፣ ማርኬቲንግ፣ ማስታወቂያና ግንዛቤ የተመራ ብራንዲንግ፣ በሸማቹ ማህበረሰብ ዘንድ ተለይቶ በመታወቅና እምነት በመፍጠር እየተስፋፋ፣ እያደገና አስተማማኝ ገበያን እያገኘ እንደሚሄድም ተነግሯል፡፡

ብራንድ የድርጅቶች መለያ እሴት የሆነና እንደ ቁሳዊ ንብረት ሁሉ በዋጋ የሚተመን ትልቅ ሃብት መሆኑ በመርሃግብሩ የተገለጸ ሲሆን፤ በዓለማችን የታዋቂ ብራንዶች ዋጋ ተተምኖ በየጊዜው ይፋ እንደሚደረግና ድርጅቶች ቁሳዊ ሃብታቸው ቢወድም እንኳን በብራንዶቻቸው ዋጋ ብቻ ማንሰራራት እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

Addis Admass

18 Feb, 05:56


390, 000, 000 ብር ደረሰ !!!!
በመላው ዓለም የሚገኙ ልበ ቀና "ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው" ያሉ ሰዎች ድጋፋቸውን ቀጥለው 390, 000, 000 (ሶስት መቶ ዘጠና ሚሊዮን) ብር መለገስ ችለዋል።
አስረኛ ቀኑን የያዘው የመቄዶንያ አረጋውያንና አእምሮ ህሙማን ማዕከል የገቢ ማሰባሰቢያ እንደቀጠለ ይገኛል። በርካታ ልበ ቀናዎች ቤታቸውን፣ ጌጣጌጦቻቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ የሚያመርቱትን ... ለማዕከሉ አበርክተዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ ሀይማኖት፣ የፖለቲካ አቋም፣ አካባቢ ሳይወስናቸው በዚህ የበጎ አገልግሎት በመሳተፍ ታሪክ እየሰሩ ሲሆን፣ ይሄ ትብብር ብዙዎችን ያበረታና መነቃቃትን የፈጠረ ሁነት ነው።
ያስጀመረን ያስጨርሰናል!!!!

Addis Admass

15 Feb, 20:32


8ተኛ ቀን ውሎ

Addis Admass

15 Feb, 20:22


ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ የሲሚንቶ ምርቱን በዕጥፍ በማሳደግ ወደ አምስት ሚሊዬን ቶን ሊያሳድግ ነው
**

የናይጀሪያው የዳንጎቴ ግሩፕ መስራችና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲግ ዋና ስራ አስፈፃሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) ጋር በኩባንያው ኢንቨስትመንት ማሻሻያ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

አሊኮ ዳንጎቴ በማብራሪያቸው በኢትዮጵያን ኢንቨስትመንታቸውን ለማስፋፋት አማራጮችን እየቃኙ መሆኑን ጠቅሰው፤ በዛሬው ዕለትም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ጋር በኢንቨስትመንት ነክ ጉዳዮች መወያየታቸውን ተናግረዋል።

ቀደም ብሎ በሲሚንቶ ኢንቨስመንት የተሰራማራው ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የተፈጠሩውን ምቹ የኢንቨስመንት ከባቢ በማየት ምርቱን በዕጥፍ ለማሳደግ መዘጋጀቱን አብስረዋል።

በዚህም ከ2 ነጥብ 5 ሚሊዬን ቶን ሲሚንቶ የማመረት አቅም ወደ አምስት ሚሊዬን ቶን እንደሚያሳድገው አብራርተዋል።

ከሲሚንቶ ባሻገር በኢትዮጵያ የግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን በሚያሳድጉ ዘርፎች ለአብነትም በአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ለመክፈት እቅድ መያዙንም አንስተዋል።

Addis Admass

14 Feb, 22:11


ሆኖም በመኖሪያ አካባቢው የተለየ ሽታ መከሰቱ ያሳሰባቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ያቀረቡትን አቤቱታ መነሻ በማድረግና ወደ አካባቢው በመሄድ የሟችን አስክሬን በማንሳት ወንጀል ፈፃሚውን በቁጥጥር ስር ያውለዋል፡፡ ተከሳሹ ላይ የሚቀሩ የምርመራዎችንና ተጨማሪ ማስረጃዎችን በማሟላት የወንጀል ድርጊቱን መፈፀሙን በሰጠው ቃል ከማረጋገጡም ባሻገር የወንጀል አፈፃፀሙን የሚመለከታቸው የሕግ ባለሙያዎችና ታዛቢዎች በተገኙበት መርቶ አሳይቷል።

ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ነሃሴ 28ቀን 2016 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ፀሀዬ ቦጋለ ጥፋተኛ ሆኖ በማግኘቱ በእድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ከተወሰነ በኋላ ውሳኔውን በመቃወም ጉዳዩን ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቀርቦ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ጥር 12 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ተከሳሽ እንዲቀጣ ወስኖበታል።

Addis Admass

14 Feb, 22:11


የባለቤቱን ህይወት በአሰቃቂ ሁኔታ ያጠፋው ተከሳሽ የሞት ፍርድ ተወሰነበት።
***
የወንጀል ድርጊቱ የተፈፀመው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ክልል ልዩ ቦታው አርሴማ ፀበል እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ ነው። ሟች ወ/ሮ አልማዝ እሸቱ ተከሳሽ ፀሀዬ ቦጋለ ከተባለው ግለሰብ ጋር ትዳር መስርተው የሚኖሩ ጥንዶች ነበሩ።

ነሀሴ 27 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሰአት ሲሆን ተከሳሽ ሟች አልማዝ እሸቱን ከሌላ ወንድ ጋር ትገናኛለሽ ስልክ ትደዋወያለሽ በሚል ጥርጣሬ ተነሳስቶ ሟች ለጉዳይዋ ከቤት ለመውጣት ልብስ ለብሳ ጫማ ለማሰር ባጎነበሰችበት ወቅት በሊጥ መዳመጫ እንጨት ማጅራቷን በመምታት ህይወቷ እንዲያልፍ በማድረግ የሟችን አስክሬን በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ባለው መጸዳጃ ቤት ውስጥ በማስገባት የግራ እግሯን ከዳሌዋ እስከ ባቷ ያለውን የሰውነት ክፍሏን በመቁረጥ፣ ስጋዋን በመመልመልና በመክተፍ የመጸዳጃ ሲንክ ውስጥ ውስጥ በመክተት ቀሪውን የሰውነት ክፍሏን ደግሞ መፀዳጃ ቤት ውስጥ ይደብቃል፤ የፖሊስ የምርመራ መዝገብ እንደሚያስረዳው ተከሳሽ ፀጋዬ ቦጋለ የአልማዝ መጥፋት ላሳሰባቸው ለቤተሰቦቿ እና ለስራ ባልደረቦቿ ገዳም እንደሄደች ለማሳመን ሞክሯል።

Addis Admass

14 Feb, 21:54


አስደናቂ ስጦታዎች እየተሰጡ ነው
የመቄዶኒያ የሁልጊዜ ደጋፊ የሆኑት ወይዘሮ ራህመት የአንገት ሃብል ጌጣቸውን ለመቄዶኒያ አበርክተዋል፡፡
ክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ ስጦታውን በቦታው በመገኘት ተረክበዋል፡፡
ያስጀመረን ያስፈፅመናል!!!

Addis Admass

14 Feb, 21:52


500ሺ ብር የመቄዶንያ የገቢ ማሰባሰብ ደምቆ ቀጥሏል።
የቫርዳስ ኢንተርቴመንት ባለቤት አቶ ተስፋ ኪሮስ የ500,000 ብር የገንዘብ ስጦታ አበርክቷል ።
ያስጀመረን ያስፈፅመናል!!!

Addis Admass

14 Feb, 21:49


የኢሲዋቲኒ ንጉስ አዲስ አበባ ገቡ


የኢሲዋቲኒ ንጉስ ምስዋቲ ሶስተኛ በ38ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።

ንጉስ ምስዋቲ ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የግብርና ሚኒስትሩ ዶ/ር ግርማ አመንቴ አቀባበል አድርገውላቸዋል ።

38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎቸ ጉባዔ "የማካካሻ ፍትሕ ለአፍሪዊያንና ዘርዓ-አፍሪካዊያን" በሚል መሪ ሃሳብ ከነገ ጀምሮ ለሁለት ቀናት ይካሄዳል፡፡

Addis Admass

14 Feb, 09:44


ኢትዮጵያ ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ፣ የአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ ጋር በመሆን ለሱዳን ሕዝብ የሰብዓዊ ድጋፍ ከፍተኛ ኮንፈረንስ በጋራ በማዘጋጀቷ ደስታ ይሰማታል። እንደ ቅርብ ጎረቤት እና እህት ሀገር ኢትዮጵያ በዚህ የፈተና ጊዜ ከሱዳን ሕዝብ ጋር በአጋርነት ትቆማለች። ሁለቱ ሀገሮቻችን በጥልቅ የተሳሰሩ በትውልዶች የጋራ ትግል፣ የጋራ ምኞት እና ባሕላዊ ቁርኝት የተጋመዱ ናቸው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ

Addis Admass

14 Feb, 07:00


264 , 000, 000 ብር !!!
በ6ተኛ ቀን የመቄዶንያ የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ላይ በአጠቃላይ 264, 000, 000 (ሁለት መቶ ስልሳ አራት ሚሊዮን) ብር የተሰበሰበ ሲሆን፣ በካሽና ዜል ከ$ 719,388 (ከሰባት መቶ ሺህ አስራ ዘጠኝ ሶስት መቶ ሰማኒያ ስምንት ዶላር) በላይ ገቢ ተደርጓል። $ 458, 262 ገንዘብ በጎ ፈንድ ሚ ማሰባሰብ ተችሏል።
በስድስተኛ ቀን ምሽት መሰናዶ ላይ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መምህር የሆኑት እና የመቄዶንያ አምባሳደር ዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ ከአእላፋት ዘማርያን ጋር በመገኘት የዝማሬ አገልግሎት እየሰጡ አድረዋል።

Addis Admass

13 Feb, 20:40


አትሌት ፅጌ ድጉማ በፈረንሳይ ሊቪ የዓለም አትሌቲክ የቤት ውስጥ ውድድር አሸናፊ ሆነች

በፈረንሳይ ሊቪ የዓለም አትሌቲክ የቤት ውስጥ ውድድር በሴቶች 800 ሜትር አትሌት ፅጌ ድጉማ አሸናፊ ሆናለች፡፡

አትሌቷ 1:59.02 በመግባት ውድደሩን ማሸነፏን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

Addis Admass

13 Feb, 20:26


በሌላ ዜና፤ በሩሲያ ለሦስት ዓመታት ታስሮ የቆየው አሜሪካዊ መምህር ማርክ ፎጌል ከትላንት በስቲያ ማክሰኞ ከእስር ተለቆ ለአገሩ አሜሪካ በቅቷል፡፡ ለታጋቹ አሜሪካዊ መምህር ከእስር መፈታት ትራምፕ ከሩሲያው መሪ ጋር የፈጠሩት ግንኙነት ወሳኝ ነበር ተብሏል፡፡

የፕሬዚዳንቱ ተፈራዳሪ ዊትኮፍ በዋይት ሃውስ በሰጡት መግለጫ፤ "ማርክ ፎጌልን ማስፈታት ወሳኝ ነበር፤ በዚህ ረገድ ሩሲያውያን በጣም፣ በጣም ተባባሪ ነበሩ" ብለዋል፡፡

የፎጌል መለቀቅ የፕሬዚዳንት ትራምፕና ፑቲን ግንኙነት ወደፊት እየጠነከረ የሚሄድ መሆኑን የሚያሳይ ነው ያሉት ዋትኮፍ፤ "መልካም ግንኙነት ነበራቸው ብዬ አስባለሁ፤ ይህም መቀጠል አለበት” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ማርክ ፎጌልን በዋይት ሀውስ ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን፤ ፎጌል ከሩሲያ እስር ነጻ ያወጡትን ፕሬዚዳንት ትራምፕና ተደራዳሪዎቹን አመስግኗል፡፡

ፎጌል ለጀርባ ህመሙ በህክምና የታዘዘ ማሪዋና ይዞ በመገኘቱ ምክንያት ነበር በሩሲያ ከ2021 ጀምሮ ለእስር የበቃው፡፡ ማርክ ፎጌልን ከእስር በመልቀቋ ሩሲያን እንደሚያደንቁ የተናገሩት ትራምፕ፤ የተደረገውን ድርድር "በጣም ፍትሃዊ" ሲሉ ገልጸውታል፤የስምምነቱን ዝርዝር ባይናገሩም፡፡

Addis Admass

13 Feb, 20:26


ሩሲያና ዩክሬን በአፋጣኝ ድርድር ለመጀመር መስማማታቸውን ትራምፕ አስታወቁ

• ፕሬዚዳንት ትራምፕና ፑቲን በሳኡዲ ተገናኝተው ሊወያዩ ነው

የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በሩሲያና ዩክሬን መካከል ጦርነቱ ቆሞ በአፋጣኝ ድርድር እንዲጀመር ሁለቱም አገራት መስማማታቸውን አስታወቁ፡፡

ትራምፕ ከሰሞኑ ከሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ባደረጉት የ1 ሰዓት ከ30 ደቂቃ የስልክ ንግግር፤ ለሦስት አመት ገደማ የዘለቀውን የሩሲያና ዩክሬን ጦርነት ለማስቆም፣ በአፋጣኝ ድርድር እንዲጀመር መስማማታቸውን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡

ለዚህም ዓላማ በቅርቡ ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር በሳኡዲ አረቢያ ተገናኝተው እንደሚወያዩ የገለጹት ዶናልድ ትራምፕ፤ በመቀጠልም አንዳቸው የሌላኛቸውን ሀገር ለመጎብኘት ስምምነት ላይ መደረሱን ይፋ አድርገዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ትራምፕ የሩሲያና ዩክሬን ጦርነትን ለማስቆም የሚያስፈልጉ ቅድም ሁኔታዎችን ባይጠቅሱም፤ የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፔቴ ሄግዘ፤ የዩክሬን የኔቶ አባልነት ጉዳይ የማይሳካ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት አሸንፈው ዋይት ሃውስ ከገቡ የዩክሬንና ሩሲያ ጦርነትን እንደሚያስቆሙ ቃል መግባታቸው የሚታወስ ነው፡፡

Addis Admass

13 Feb, 20:26


”የዓድዋ ድል የአንድነትና የጽናት ተምሳሌት ነው”
የባርባዶስ ጠ/ሚኒስትር


የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ለመሳተፍ ወደ አዲስ አበባ የመጡትን የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞተሌን የዓድዋ ድል መታሰቢያን አስጎብኙ፡፡

የዓድዋ ድል መታሰቢያን በመጎብኘታቸው የተሰማቸውን ደስታ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሯ፤ የዓድዋ ድል የአንድነትና የጽናት ተምሳሌት እንዲሁም በትብብር ማንኛውንም ሃይል የማሸነፍ ምልክት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ ሞተሌ፣ በዓድዋ ጀግኖች ሐውልት ስርም የአበባ ጉንጉን ማኖራቸውን የከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል።

Addis Admass

08 Feb, 21:37


https://youtu.be/q0bMjwt9PvM

Addis Admass

08 Feb, 21:29


በ800 ሜትር የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና አትሌት ፅጌ ድጉማ ድል ቀናት

በፈረንሳይ ሜዝ በተካሄደ የ800 ሜትር የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ውድድር እትሌት ፅጌ ድጉማ አሸንፋለች፡፡ ፅጌ የ800 ሜትሩን 1 ደቂቃ ከ58 ሴኮንድ ከ97 ማይክሮ ሴኮንድ በመጨረስ በቀዳሚነት ማጠናቀቋን የዓለም አትሌቲክስ መረጃ ያመላክታል፡፡

Addis Admass

08 Feb, 20:15


ሊያና ሄልዝ ኬር በደቡብ ሱዳን እና ሶማሊላንድ ስራ ለመጀመር ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝ ዶክተር ግርማ አስታውቀው፣ በሐዋሳ ሶስት ትልልቅ ሆስፒታሎች እና የዳይግኖስቲክስ ማዕከላት፣ የኦክስጂን ፋብሪካ፣ የመድሐኒት እና የሕክምና መሳሪያዎች አስመጪ እና ማከፋፈያ፤ እንዲሁም አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች አራት የሕክምና ማዕከላት እንዳሉት ገልጸዋል። ተቋሙ ወደፊት የኩላሊት፣ የጉበት እና የሌሎች ንቅለ ተከላ ሕክምናዎችን ለመስጠት የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኙ እና ከመንግስት በኩል ለሕክምናው አጋዥ የሆኑ የሕግ ማዕቀፎች በምክር ቤት ጸድቀው ወደ ስራ ሲገቡ ወዲያውኑ አገልግሎት ለመስጠት እንደተዘጋጀ ስራ አስፈጻሚው አመልክተዋል።
ከጋዜጣዊ መግለጫው ባሻገር፣ ለተቋሙ የተሰጡት የዕውቅና ሰርተፊኬቶች በክብር ዕንግዶች እጅ ለስራ አስፈጻሚው ዶክተር ግርማ አባቢ የተበረከቱ ሲሆን፣ ተቋሙ ከዚህ የበለጠ ደረጃ ላይ እንዲደርስ በጥብቅ መንቀሳቀስ እንዳለበት ተነግሯል።

Addis Admass

08 Feb, 20:15


የጥራት ዕውቅናው ተቋሙ በዚሁ ዓላማ ተግቶ ለመስራቱ ማሳያ መሆኑን የተናገሩት ዶክተር ግርማ፣ “ተቋሙ በአንድ ጊዜ አራት ዓለም አቀፍ ዕውቅና አግኝቷል” ብለዋል። አክለውም፣ “በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ በሕክምና ዘርፍ የተሰጠ የዕውቅና ሰርተፊኬት ነው” በማለት ተቋሙ ስላገኘው የጥራት ዕውቅና አስረድተዋል።

በሊያና ሄልዝ ኬር ስር የሚገኘ ያኔት ሆስፒታል ዕውቅና ያገኘባቸው ዘርፎች ሶስቱ በኮርፖሬት አመራር፣ በመጀመሪያና ከፍተኛ ደረጃ ህክምናዎች የISO 9001-2015 የጥራት አመራር ስርዓት ዕውቅና፣ እንዲሁም በላብራቶሪ ጥራት አመራር የISO 15189-2015 አክርዲቴሽን መሆናቸውን በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ ተጠቅሷል። በዚሁ ለተቋሙ ከተሰጠው ዕውቅና ውስጥ በክሊኒካል ኬሚስትሪ ዓለምአቀፍ ሰርተፊኬት ማግኘቱን ዶክተር ግርማ አብራርተዋል።

Addis Admass

08 Feb, 20:14


ሊያና ሄልዝ ኬር በደቡብ ሱዳን እና ሶማሊላንድ የሕክምና ማዕከላትን ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ አስታወቀ

ሊያና ሄልዝ ኬር በደቡብ ሱዳን እና ሶማሊላንድ የሕክምና ማዕከላትን ለመክፈት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ አስታውቋል። ተቋሙ በኢትዮጵያ “የመጀመሪያ ነው” የተባለላቸውን ከሕክምና ጥራት እና ተያያዥ አገልግሎቶች ጋር የተገናኙ ዕውቅናዎችን እንዳገኘ ገልጿል።

ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ አያት አካባቢ በሚገኘው እና በሊያና ሄልዝ ኬር ስር በሚንቀሳቀሰው ያኔት ሆስፒታል ጋዜጣዊ መግለጫ የተሰጠ ሲሆን፣ በመግለጫውም ላይ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ወይዘሮ ፍሬሕይወት አበበ፣ የሊያና ሄልዝ ኬር መስራች እና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ግርማ አባቢ እና የኢትዮጵያ አክሪዲቴሽን አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ ቦንሳ ባይሳ ተገኝተው ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ሰጥተዋል። የተቋሙ ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ግርማ አባቢ፣ ለአንድ ማሕበረሰብ ጥራት ወሳኝ እንደሆነ አውስተው፣ ሊያና ሄልዝኬር ባለፉት 13 ዓመታት ጥራትን መሰረት አድርጎ ሲሰራ መቆየቱን ጠቅሰዋል።

Addis Admass

08 Feb, 19:58


በገንዘብ ዕርዳታው መቋረጥ የተጎዱ ድርጅቶች አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን የሚያገኙበትና ችግሩን የሚቋቋሙበትን መንገድ የሚያፈላልግ አንድ ቡድን ማቋቋሙን ምክር ቤቱ በዚሁ መግለጫው ላይ ጠቁሟል። በተጨማሪም፣ ይህንኑ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት አንድ የምክክር መድረክ በቅርብ ቀናት ውስጥ ለማዘጋጀት ማቀዱን አስታውቋል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበራት ድርጅቶች ምክር ቤት ከ4 ሺሕ 400 በላይ የሲቪል ማሕበራትን በስሩ አቅፎ የሚንቀሳቀስ ተቋም መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
በተያያዘ ዜና የኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ባለፈው ማክሰኞ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ ከሰሞኑ በዩ ኤስ ኤ አይ ዲ በኩል ለኢትዮጵያ ሲደረግ የነበረው ዕርዳታ እንደተቋረጠ መገንዘቡን ገልጾ፣ ከዚህ ጋር በተያያዘም በተራድዖ ድርጅቱ የገንዘብ ድጋፍ ያገኙ የነበሩ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ንብረትና ገንዘብ ላይ ዕግድ ጥሏል።
አያይዞም በአሁኑ ወቅት ከዩ ኤስ ኤ አይ ዲ የገንዘብ ድጋፍ የሚያገኙ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ያለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ግልጽ ፈቃድ ንብረት የማስተላለፍ፣ የማስወገድ ወይም የመሸጥ ወይም ከመደበኛ የፕሮጀክት ስራዎች ጋር ተያያዥ ከሆኑ ጉዳዮች ውጪ፣ በማንኛውም መንገድ ንብረትና ገንዘብ ለሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ እንደማይችሉ በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ባለስልጣኑ አክሎም፣ የኢትዮጵያ መንግስት የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ከየትኛውም ሕጋዊ ምንጭ ሃብት በማሰባሰብ፣ ሕጋዊና ሞራላዊ በሆኑ ዓላማዎች ላይ መስራት እንደሚችሉ የሚደነግግ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ዓዋጅ 1113/2011 አውጥቶ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አውስቷል።
ለሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባስተላለፈው በዚህ አስቸኳይ መግለጫ፣ ከዕግድ ውሳኔው በተጨማሪ፣ ማሳሰቢያውን ተላልፈው በሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች ላይ ባለስልጣኑ ዓይነቱን በግልጽና በዝርዝር ያላስቀመጠውን “ተገቢውን ዕርምጃ” እንደሚወስድ አሳስቧል።

Addis Admass

08 Feb, 19:58


በዩኤስኤአይዲ የገንዘብ ድጋፍ መቋረጥ ለተጎዱ ድርጅቶች
አማራጭ የገንዘብ ምንጮችን የሚያፈላልግ ቡድን ተቋቋመ
በአሜሪካ ዓለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅት (ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ) የገንዘብ ድጋፍ መቋረጥ ምክንያት ለተጎዱ ድርጅቶች አማራጭ የገንዘብ ምንጭችን የሚያፈላልግ ቡድን መቋቋሙ ተገልጿል። ይኸው ቡድን የተቋቋመው በኢትዮጵያ ሲቪል ማሕበራት ድርጅቶች ምክር ቤት አማካይነት ነው።
በዶናልድ ትረምፕ የሚመራው የአሜሪካ መንግስት ጥር 12 ቀን 2017 ባስተላለፈው ትዕዛዝ መሰረት የተራድዖ ድርጅቱ የሚሰጣቸው ዘርፈ ብዙ ድጋፎች መቋረጣቸውን ያወሳው ምክር ቤቱ፣ በተለይም በሰብዓዊ መብቶች፣ ዴሞክራሲ፣ ልማት፣ ትምሕርት እና ጤና ላይ የሚሰሩ ድርጅቶችን እንደጎዳ አስታውቋል። ምክር ቤቱ አያይዞም፣ በድርጅቱ ገንዘብ የሚደገፉ ፕሮጀክቶች ስራ ማቆማቸው “በእጅጉ አሳስቦኛል“ ብሏል።
ባለፈው ረቡዕ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ምክር ቤቱ ባወጣው መግለጫ እንዳብራራው፣ ዩ ኤስ ኤ አይ ዲ የገንዘብ ዕርዳታውን በድንገት ማቆሙን ተከትሎ፣ በድርጅቱ የገንዘብ ድጋፍ በሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶችና ድርጅቶቹ ድጋፍ በሚያደርጉላቸው የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳርፋል። ምክር ቤቱ የአሜሪካ የተራድዖ ድርጅት ለበርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ በሚከናወኑ የሰብዓዊ እና ልማት ስራዎችን በዋናነት ሲደግፍ መቆየቱን አመልክቷል።
⬇️⬇️

Addis Admass

08 Feb, 19:52


መጽሐፉ በንባብ ይለቅ!

ሌሊሳ ግርማን በደንብ አውቀዋለሁ፡፡ በደራሲነቱ ብቻ ሳይሆን እንደ ሰውም - እንደ ጓደኛም ነው የማውቀው፡፡ የአዲስ አድማስ የረዥም ጊዜ አምደኛም ነው፡፡ የጋዜጣው ቤተሰብ ነው ቢባል ይቀላል፡፡ ለበርካታ ዓመታት ብዙ ጊዜውን በአዲስ አድማስ ቢሮ ነበር የሚያሳልፈው፤ በመጻፍና በጥበባዊ ሃሳቦች ላይ ውይይትና ክርክር በማድረግ፡፡ የሚገርመኝ ግን ተቀጥሮ የሰራበት ጊዜ አለመኖሩ ነው፡፡ የሙሉ ጊዜ ደራስያን ከሚባሉት የሚመደብም ቢሆን ሁሌም በፍሪላንሰርነት ነው የሚጽፈው፡፡ ተቀጥሮ መሥራት ነጻነትን ይጋፋል ብሎ ሳያስብ አይቀርም፡፡
ሌሊሳ እስካሁን ቀላል የማይባሉ የአጭር ልብወለድና ወግ ስብስቦችን ለአንባቢያን አድርሷል፡፡ ትጉህ የጥበብ ገበሬ ነው፡፡ አሁን ደግሞ በረዥም ልብወለድ ለመጀመሪያ ጊዜ መጥቷል፡፡ እኔ አዲሱን ልብወለድ ማንበብ ጀምሬአለሁ፡፡ የመጀመሪያዎቹን 50 ገጾች በጉጉትና ሳላርፍ ነው ያነበብኩት፡፡ ለየት ያለ ታሪክ ይመስላል - ከአጀማመሩ፡፡ ጥልቅ ሃሳቦችን ያጨቀ ቢሆንም አዝናኝም ጭምር ነው፤ማህበራዊ ሂስና ስላቅም በሽበሽ ነው፡፡

በአጭሩ ምን ለማለት ነው? ሌሊሳን አንብቡት - “በታችም በምድር” ይነበብ እያልኩ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ለወዳጄ ሌሊሳ እንኳን ደስ ያለህ - Congra! ልለው እወዳለሁ፡፡ ከዚህ በላይ ደስታና የምስራች ከየት ይመጣል!
መጽሐፉ በንባብ ይለቅ ብያለሁ!
ኢ.ካ

Addis Admass

08 Feb, 19:49


የአለማችን ቀዳሚዋ ኮኬይን አምራችና ለውጭ ገበያ አቅራቢ የሆነችው ኮሎምቢያ፣ የኮኬይን ንግድን ህገወጥ ነው ብትልም፣ በ2022 ብቻ ከእጹ የወጪ ንግድ 18 ነጥብ 2 ቢሊየን ዶላር ማግኘቷን ብሉምበርግ ያወጣው መረጃ ያመላክታል።

የኮሎምቢያ ኮኬይን ቀዳሚ መዳረሻ የሆነችው አሜሪካ፤ የደቡብ አሜሪካዋን ሀገር የኔቶ አባል ያልሆነች ዋነኛ አጋር አድርጋ በተለይ በአደንዛዥ የእጽ ዝውውር በትብብር ትሰራለች።

ይሁን እንጂ በበርካታ ሀገራት ህገወጥ የሆነውን አደንዛዥ እጽ ዝውውር መግታት ላይ የሚጠበቀውን ውጤት እንዳላመጡ የሀገራቱ መሪዎች ያምናሉ።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኮኬይን በአለማችን በብዛት ጥቅም ላይ ከሚውሉ አደንዛዥ እጾች አራተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝና በርካታ የጤና እክሎችን እንደሚያስከትል ይገልጻል። ኮኬይን እረፍት የለሽ ህመም ላለባቸው ሰዎች በመድሀኒት መልክ በሀኪሞች አማካኝነት እንደሚሰጥ ይታወቃል።
(DW)

Addis Admass

08 Feb, 19:49


የኮሎምቢያው ፕሬዚዳንት ኮኬይን "ከውስኪ የከፋ አይደለም" አሉ

• ኮኬይን በዓአለማቀፍ ደረጃ ህጋዊ እንዲሆን ጠይቀዋል


የኮሎምቢያው ፕሬዚዳንት መንግሥታቸው ስርጭቱን መቆጣጠር ያልቻለውን ኮኬይን፤ "ከውስኪ የከፋ አይደለም" የሚል አስተያየት መስጠታቸው አነጋጋሪ ሆኗል።

ፕሬዚዳንቱ ከሰሞኑ በቴሌቪዥን በተላለፈ የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ፤ "ኮኬይን ህገወጥ የሆነው በላቲን አሜሪካ ስለሚመረት እንጂ ከውስኪ የከፋ ጉዳት ኖሮት አይደለም" ብለዋል።

በየትኛው የምርምር ጽሁፍ ላይ እንደወጣ ሳይጠቅሱም፤ "ተመራማሪዎች ይህንኑ አረጋግጠዋል" ብለዋል፤ በንግግራቸው፡፡

ፕሬዚዳንት ጉስታቮ ፔድሮ፣ አለማቀፉን የኮኬይን ኢንዱስትሪ በቀላሉ ለማፈራረስ አደንዛዥ እጹ ህጋዊ እንዲሆንም ጠይቀዋል።

"ሰላም ከፈለጋችሁ፤ የአደንዛዥ እጽ ንግድ መረብን መበጣጠስ ካሻችሁ ኮኬይን በአለማቀፍ ደረጃ ህጋዊ መሆን አለበት፤ ከዚያ ልክ እንደ ወይን ይሸጣል" ሲሉም ተደምጠዋል።

ፕሬዚዳንቱ አክለውም፤ "ፌንታይል" የተሰኘው አደንዛዥ እጽ ግን "አሜሪካውያንን እየገደለ የሚገኝ ነው፤ በኮሎምቢያ የሚሰራ አይደለም" ብለዋል።

ግራ ዘመሙ መሪ በ2022 ዓ.ም ስልጣን ከያዙ ጀምሮ በአደንዛዥ እጽ ዝውውር ላይ ጠንካራ ዘመቻ እንደሚከፍቱ ቢገልጹም፣ የኮኬይን ምርት እየጨመረ እንጂ እየቀነሰ አልሄደም ይላል የሲኤንኤን ዘገባ።

በ2023 ዓ.ም ከ253 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በኮካ ቅጠል ተሸፍኖ ከ2 ሺህ 600 ሜትሪክ ቶን በላይ ኮኬይን ተመርቷል፤ ይህም ከ2022ቱ በ53 በመቶ መጨመሩን ዘገባው ያክላል።

Addis Admass

08 Feb, 19:46


የጊፍት ሪልስቴት ባለቤት አቶ ገብረየስ ኢጋታ ለመቄዶንያ የ12 ሚሊዮን ብር ቤት በስጦታ አበረከቱ።
ዛሬ በተጀመረው የሐብት ማሰባሰብ መርሐ-ግብር ተገኝተውም ቁልፉን አስረክበዋል።

Addis Admass

08 Feb, 19:41


የአይ.ኤም.ኤፍ. ማኔጂንግ ዳይሬክተር ለሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል


የዓለም አቀፉ ገንዘብ ተቋም (አይ ኤም ኤፍ) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ለሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ዛሬ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ በቆይታቸውም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድና ከከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እድገት፣ ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፖሊሲዎችና በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በጉብኝታቸው ወቅት ከግሉ ዘርፍ ተወካዮች ጋር በኢትዮጵያ ስላለው የንግድ ሁኔታና በኢኮኖሚ እድሎች ዙሪያ ውይይት ያደርጋሉ ተብሏል፡፡

ዋና ዳይሬክተሯ እ.ኤ.አ በ2019 የተቋሙ ኃላፊ ከሆኑ በኋላ፣ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ የመጀመሪያቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይ ኤም ኤፍ)፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና የገንዘብ ድርጅት ሲሆን፣ በ191 አባል ሀገራት የሚደገፍና ዋና መስሪያ ቤቱን በዋሽንግተን ዲሲ ያደረገ ተቋም ነው፡፡

Addis Admass

07 Feb, 20:06


"መሪው" ምድርን ለቅቆ
ከሰው ርቆ
አየር ላይ ተንሳፎ
ሰማይ ላይ ሰፍፎ
ቁልቁል እያየ
ልቡ ታበየ
ህዝቡ ግና እየሳቀ
"ገለባ በንፋስ ከፍ ስላለ"
አይደንቅም አለ

Addis Admass

07 Feb, 20:05


አሜሪካ የአውሮፕላን አደጋ ደጋገማት

በአሜሪካዋ አላስካ 10 መንገደኞችን የጫነች አውሮፕላን የገባችበት መጥፋቱ ተነገረ፡፡

ባለፈው ሳምንት አንድ የአሜሪካ አየር መንገድ ንብረት የሆነ የመንገደኞች አውሮፕላን ከአነስተኛ ወታደራዊ ሄሊኮፕተር ጋር ተጋጭታ የ67 መንገደኞች ህይወት ማለፉ ይታወቃል፡፡

በተጨማሪም፣ ባሳለፍነው ሳምንት የአምቡላንስ አገልግሎት የምትሰጥ አነስተኛ አውሮፕላን በመኖሪያ ህንጻ ላይ ተከስክሳ የአራት ሰዎች ህይወት አልፏል።

በትናንትናው ዕለት ደግሞ የአሜሪካ ወታደራዊ አነስተኛ አውሮፕላን በፊሊፒንስ ተከስክሳ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነግሯል፡፡

አሁን ደግሞ ከእነአብራሪው አሥር ሰዎችን ይዛ ስትጓዝ የነበረች አነስተኛ የመንገደኞች አውሮፕላን የገባችበት መጥፋቱ ተነግሯል።

የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የጠፋችውን አውሮፕላን እየፈለጉ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

Addis Admass

07 Feb, 20:02


ከአሜሪካ ጋር መነጋገር እንደማያዋጣ በልምድ አረጋግጠናል- የኢራኑ ጠቅላይ መሪ


የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሚኒ፣ ከአሜሪካ ጋር መነጋገር እንደማያዋጣ በልምድ አረጋግጠናል ሲሉ ተናገሩ።

"ከአሜሪካ ጋር የሚደረግ ድርድር አሪፍ፣ ብልህና ክብር የሚገባው አይደለም። የትኛውንም ችግራችንን አይፈታም። ምክንያቱም ከልምድ አይተነዋል" ብለዋል፤ ካሚኒ።

ትራምፕ በመጀመሪያ የስልጣን ዘመናቸው ወቅት በ2018 ዓ.ም፣ አሜሪካን ቴህራን ከአለም ኃያላን ሀገራት ጋር ከደረሰችው የ2ዐ15ቱ የኑክሌር ስምምነት አስወጥተው፣ የኢራን ኢኮኖሚን እያሽመደመደ ያለውን ማዕቀብ በድጋሚ ጥለውባታል።

ኢራን ከሁለት አመት ንግግር በኋላ ከአሜሪካና ሌሎች ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ ብትደርስም አሜሪካ በስምምነቱ መገዛት አልቻለችም ብለዋል።

"ኃላፊነት ያለበት ሰው ስምምነቱን ቀዶ ጥሎታል" ብለዋል፤ ካሚኒ ትራምፕን በማመላከት።

በሌላ በኩል፤ አንድ ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣን ለሮይተርስ እንደተናገሩት፤ ኢራን አሜሪካ አለመግባባቶቹን እንድትፈታ እድል ለመስጠት ዝግጁ ናት።

"የኢራንን ደህንነት ስጋት ውስጥ የሚጥሉ ከሆነ፣ የእነሱን ደህንነት አደጋ ውስጥ እንጥለዋለን። ማስፈራራታቸውን የሚቀጥሉ ከሆነ እኛም እንገፋበታለን።" ብለዋል፤ ባለሥልጣኑ፡፡

ትራምፕ ስላነሱት በጋዛ ያሉ ፍልስጤማውያንን ወደ ሌላ ሀገር የማዛወር ጉዳይ በተመለከተ ካሚኒ ሲናገሩ፤ "በወረቀት ላይ ካየነው አሜሪካ የአለምን ካርታ ቀይራለች፤ ወረቀት ላይ ብቻ ነው፤ ምክንያቱም ከእውነታው ጋር አይጣጣምም" ብለዋል።

(አል ዐይን)

Addis Admass

07 Feb, 20:01


የኢትዮጵያ የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ፣ ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ለአስራ ሁለቱ ክልሎችና ሁለት የከተማ አስተዳደሮች በጻፉት ደብዳቤ፤ በአሜሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (CDC) እና በአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት (USAID) “የበጀት ድጋፍ በኮንትራት የተቀጠሩ ሠራተኞች ውል እንዲቋረጥ” አሳውቀዋል።

የኮንትራት ሠራተኞቹ ውል የሚቋረጠው የአሜሪካ መንግሥት በሁለቱ ተቋማት “አማካይነት በተገኘ የበጀት ድጋፍ የሚከናወን ማንኛውም ሥራም ሆነ ክፍያ” ከጥር 16 ቀን 2017 ጀምሮ “እንዲቋረጥ ማሳሰቢያ” በመስጠቱ መሆኑን ዶክተር ደረጀ በደብዳቤው ገልጸዋል።

ፔፕፋር (PEPFAR) ተብሎ በሚጠራው የኤድስ ሥርጭትን መከላከያ መርሐ-ግብር እ.ኤ.አ በ2024 ብቻ ለ3.6 ሚሊዮን ሰዎች የምርመራና ማማከር፣ ከ520,000 በላይ ሰዎች ደግሞ የሕክምና አገልግሎት መቅረቡን ባለፈው ወር በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ አስታውቀው ነበር።

አምባሳደሩ እንዳሉት፤ ባለፉት ሁለት አስርት ዓመታት፣ በአሜሪካ ተራድዖ ድርጅት (USAID) በኩል ለጤናው ዘርፍ 4 ቢሊዮን ዶላር ገደማ፤ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ሥርጭትን ለመግታት በተዘረጋው ፔፕፋር በኩል በአንጻሩ 3 ቢሊዮን ዶላር አሜሪካ ለኢትዮጵያ ድጋፍ አድርጋለች።

(DW)

Addis Admass

07 Feb, 20:01


በኢትዮጵያ የ5ሺ የጤና ሠራተኞች ውል መቋረጡን
የተባበሩት መንግሥታት ኃላፊ አረጋገጡ


በኢትዮጵያ የ5ሺ የመንግሥት የጤና ሠራተኞች ውል መቋረጡን በተባበሩት መንግሥታት የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ሥርጭት መከላከያ ፕሮግራም (UNAIDS) ምክትል ኃላፊ ክሪስቲን ስቴግሊንግ አረጋገጡ።

አሜሪካ የምትሰጠውን የውጪ ዕርዳታ ስታቋርጥ፣ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ሥርጭትን ለመግታት የተዘረጉ መርሐ ግብሮች እንዳይካተቱ የተላለፈ ውሳኔ ቢኖርም፣ “ከፍተኛ ግራ መጋባት” መፍጠሩን ኃላፊዋ ተናግረዋል።

መድሐኒት ለማኅበረሰብ የማጓጓዝ ሥራና የማኅበረሰብ ጤና አገልግሎት ሠራተኞች የአሜሪካ መንግሥት ባስተላለፈው ውሳኔ ተጽዕኖ ውስጥ የወደቁ መሆናቸውን ኃላፊዋ ዛሬ አርብ በጄኔቫ ለጋዜጠኞች አስረድተዋል።

የአሜሪካዉ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሐገራቸዉ ለዉጪ የምትሰጠዉን በመቶ ሚሊዮን ዶላሮች የሚቆጠር ዕርዳታ ለ90 ቀናት እንዲቆም ያዘዙት ወደ ዋይት ሐውስ እንደተመለሱ ነው። ከትራምፕ ትዕዛዝ በኋላ የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤት፣ ትዕዛዙ ፔፕፋር (PEPFAR) ተብሎ በሚጠራው የኤድስ ሥርጭትን ለመከላከል የተበጀ የድጋፍ መርሐ-ግብር እንዳያካትት የሚያደርግ ውሳኔ አሳልፎ ነበር።

የአሜሪካ ውጪ ጉዳይ መሥሪያ ቤትን እርምጃ በበጎ እንደሚመለከቱ የጠቀሱት ክሪስቲን ስቴግሊንግ፤ ይሁንና ሁኔታው አሁንም በውዥንብር የተሞላ እንደሆነ ተናግረዋል።

“በኢትዮጵያ በአሜሪካ እርዳታ የሚደገፉ 5,000 የመንግሥት የጤና ሠራተኞች ውሎች አሉን። እነዚህ ሁሉ ተቋርጠዋል” ሲሉ ተናግረዋል።

Addis Admass

07 Feb, 19:58


ከንቲባ አዳነች፤ ከኮማንዶና አየር ወለድ እዝ የሰራዊት አመራሮች
ጋር በአድዋ ድል መታሰቢያ

የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የኮማንዶና አየር ወለድ እዝ የሰራዊት አመራሮችን በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተቀብለው ተወያዩ፡፡

የኮማንዶና አየር ወለድ እዝ ዋና አዛዥ ሌ/ጀ ሹማ አብደታ በዚህ ወቅት፤ የዓድዋ ድል መታሰቢያ ምንም አይነት ልዩነት ቢኖር በሀገር ጉዳይ በጋራ በመቆም ፈተናዎችን የማለፍ ተምሳሌት መሆኑን ተናግረዋል::

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በበኩላቸው፤ የኮማንዶና አየር ወለድ እዝ የሰራዊት አመራሮችና ሰራዊቱ ለሀገር እየከፈሉት ላለው ውድ ዋጋ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

የዓድዋ ድል መታሰቢያ፣ ለሀገር ውለታ የዋሉ ጀግኖች ቋሚ መታሰቢያ መሆኑንም ከንቲባዋ አውስተዋል፡፡

Addis Admass

06 Feb, 19:33


አንዳንድ ሰዎች መኪና እየነዱ በእጃቸውም በአፋቸውም ሊሳደቡ ይችላሉ። እኔ መልሼ እንደነሱ ማድረግ አልችልም። ምንም አይነት ብሽቅ ይግጠመኝ ዋጥ አድርጌው አልፋለሁ። አንድ ጊዜ ሮብ ምሽት የእግዚአብሔርን ቃል ለማካፈል ወደ አንድ ቤተክርስቲያን እየነዳሁ እያለ ከጎኔ የመጣ መኪና በጣም በሚያበሳጭ ሁኔታ ከፊቴ ጥልቅ ብሎ ገባ። እግዚአብሔር ሲረዳኝ፤ "አይዞህ ችግር የለም! It's Ok!" አልኩት ..... የሚሾፍረውን ሰው። ሦስት ሰዎችን ጭኗል! መንገዱን ቀጠለ.... እኔም ቀጠልኩ። ከፊትለፊቴ ሲሄዱ ቆዩና እኔ እየሄድኩበት ወደነበረው ቤተክርስቲያን ግቢ አዙረው ገቡ። ለካ እነሱ የእኔን ስብከት ለመስማት ወደ ቤተክርስቲያን እየሄዱ ነበር። ስሜታዊ ሆኜ ተናግሬያቸው ቢሆንስ? ለማስተማር መድረኩ ላይ ስቆም እንዴት በተቸገሩ ነበር!

(የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ታላቅ አእምሮ፤በዶ/ር ወዳጄነህ መሐረነ፤ገፅ 45)

(ምንጫችን Kibru Books ቴሌግራም ቻናል ነው፡፡ ክብሩ ትራኮን ህንጻ 1ኛ ፎቅ ላይ የመጻህፍት መሸጫ መደብር ያለው ሲሆን፤ በቴሌግራም ቻናሉ ደግሞ ከየመጻህፍቱ መርጦ የቀነጨባቸውን ማራኪ አንቀጾች አንብቡልኝ ሲል ይጋብዛል፡፡ ቻናሉን ጎብኙለት፤ሰብስክራይብም አድርጉት፤ታተርፉበታላችሁ፡፡)

Addis Admass

06 Feb, 19:33


የሚዋጉበትን ጦርነት መምረጥ !

ሔሮድስ ህፃኑን ኢየሱስን ለመግደል ፍለጋ ጀመረ። ዮሴፍና ማርያምም ዮሴፍ ባየው ህልም መሰረት ህፃኑን ይዘው ወደ ግብፅ ሸሹ። (ማቲ2:13) ግን ለምን ሸሹ? ሔሮድስን ለምን አልተጋፈጡትም? ምነው ዮሴፍ ወንድ አይደል እንዴ! እንዴት ይሸሻል? ዞር ማለትን ለምን መረጡ?

አንዳንድ መጋፈጥ ያለብን ሁኔታዎች አሉ፤ አንዳንዱን ግን እንሸሸዋለን! በመንገድ ላይ ተሳዳቢ ሰዎች ቢሰድቡኝ ቆሜ አልሰዳደብም... ወይም አልደባደብም። ያንን ባደርግ ችግር ውስጥ እምገባው እኔው መሆኔን አውቃለሁ። ጉልበት በዝቶልኝ ብደበድብ.... እስር ቤት እገባለሁ!...... ብደበደብ ደሞ እዋረዳለሁ! ደግሞ እኔ ልሞክረው ብልም መደባደብ አልችልበትም። ስለዚህ በሰላም ከዚያ ስፍራ ዞር ማለት ነው ያለብኝ! አያድርገውና አልፈው ከመጡ..... ፖሊስ መጥራት ጥሩ መፍትሔ ነው!

Addis Admass

06 Feb, 15:02


ቴዲ አፍሮ ለጋሽ መሐሙድ አህመድ ስጦታ አበረከተ
ተወዳጁ ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ፣ ለአርቲስት መሀሙድ አህመድ የስሙ የመጀመሪያ ፊደል «M» ያለበትን በወርቅ የተጌጠ ከዘራ በስጦታ አበረከተለት፡፡

Addis Admass

06 Feb, 14:49


የሌሊሳ ግርማ “በታችም በምድር” ነገ በገበያ ላይ ይውላል


በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የደራሲ ሌሊሳ ግርማ “በታችም በምድር” የተሰኘው ወጥ የልቦለድ መፅሐፍ በነገው ዕለት በገበያ ላይ ይውላል፡፡

በተለያዩ መጣጥፎችና አጭር ልብ ወለድ ጽሁፎች በአንባቢያን ዘንድ ተወዳጅነትን ያተረፈው ሌሊሳ ግርማ፤ አሁን ደግሞ በመጀመሪያ የወጥ ልቦለድ ድርሰት መጥቻለሁ እያለ ነው፡፡

ደራሲ ሌሊሳ ግርማ፤ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ በሚያቀርባቸው ጥበባዊ መጣጥፎቹም ይታወቃል፡፡

ደራሲው ከዚህ ቀደም “የንፋስ ህልም እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች”፣ “አፍሮ ጋዳ”፣ “መሬት - አየር - ሰማይ”፣ “የሰከረ እውነታ”፣ “እስቲ ሙዚቃ”፣ “ነፀብራቅ”፣ “ይመስላል ዘላለም”፣ የሚሰኙ የመጣጥፍና የአጭር ልብ ወለድ ስብስብ መድበሎችን ለአንባቢያን ማበርከቱ ይታወሳል፡፡

የመጽሐፉ አሳታሚ ዋሊያ መፅሐፍት ድርጅት ሲሆን፤ መጽሐፉ ከነገው ዕለት ጀምሮ በከተማዋ በሚገኙ መጻሕፍት ቤቶች ሁሉ ለገበያ እንደሚውል ታውቋል፡፡

Addis Admass

06 Feb, 14:47


ማህበሩ በየወሩ ከ25 ሚሊየን ብር በላይ በመመደብ 5800 ለሚሆኑ ቤተሰቦቹ ቋሚ ድጋፍ ከማድረጉ በተጨማሪ በዛሬው ዕለት ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም 10 ሚሊየን ብር በመመደብ የማዕድ ማጋራት ስነ ስርዓት ከማካሄዱ በተጨማሪ 13 ለሚደርሱ አካል ጉዳተኞች የዊልቸር እና 25 ለሚደርሱ ቤተሰቦች ደግሞ ሙሉ የቤት እቃ ድጋፍ አድርጓል።

በመርሀ ግብሩ ላይ ፣ ሁሌ ድጋፍ የሚያደርግላቸው የመቄዶንያ የአዕምሮ ህሙማን ማዕከል ተወካዮች፣ የባቡል ኸይር መስራች ፣ የሙዳይ በጎ አድራጎት መስራች ፣ የሜሪጆይ መስራች፣ የጌርጌሴኖን መሥራች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሚዲያ አካላት በቦታው ተገኝተዋል።

ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር፤ በሰኔ ወር 2016 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማኅበራት ማደራጃ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣውን የማኅበራት ምዝገባ መስፈርቶችን በማሟላት ሕጋዊ ዕውቅናና ፈቃድ የተሰጠው መሆኑ ይታወቃል።

Addis Admass

06 Feb, 14:46


ፍኖተ ጽድቅ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ በመመደብ የነዳያን ምገባ አካሄደ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ከጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች ጋር በመሆን፣ ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ባዘጋጀው በነዳያን ምገባ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው ነዳያንን በመመገብ፣ ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል።

በቅዱስነታቸው የሚመራው የልዑካን ቡድን በስፍራው ሲደርስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ሲቲ አህገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የማኅበሩ መስራችና የቦርድ ሰብሳቢ መጋቢ አእላፍ ጸጋዬ ደበበ፣ የማኅበሩ ሥራ አስኪያጅ መምህር ኤልያስ ሙላቱና የማኅበሩ አባላት ደማቅና መንፈሳዊ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በዚሁ ጊዜም ህጻናት እቅፍ አበባ ያበረከቱ ሲሆን፤የማኅበሩ ዘማርያንም መንፈሳዊ መዝሙር በመዘመር ከፍተኛ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

Addis Admass

05 Feb, 20:14


የአሜሪካው የስለላ ተቋም (ሲአይኤ) ሠራተኞቹ ሥራ እንዲለቁ እየጠየቀ ነው
********************

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የፌዴራል ሠራተኞችን ቁጥር ለመቀነስ የያዙትን ዕቅድ ለማስፈፀም ሲአይኤን ቀዳሚ አድርገዋል።

ሠራተኞቹ በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን የሚለቁ ከሆነ የ8 ወር ደመወዝ እና ጥቅማጥቅማቸውን እንደሚያገኙ ተነግሯቸዋል።

የተቋሙን ሠራተኞች ይመለከታል የተባለው የፌደራል ሠራተኞች ቅነሳ ዕቅድ የተቋሙን አንዳንድ የሥራ ክፍሎች እና ሞያዎች ግን አይመለከትም ተብሏል።

ይህ ቅነሳ የትራምፕ የፌደራል መንግሥት ሰራተኞችን የመቀነስ አጀነዳ ጥረት መሆኑም ተነግሯል።

ፕሬዝዳንት ትራም በፌደራል ሠራተኞች ቅነሳ ዕቅዳቸው በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን የሚለቁ ሠራተኞች የ8 ወር ደመወዛቸውን ከነጥቅማጥቅሙ እንደሚወስዱ አሳውቀው ነበር።

ብዙ ተቋማት ጉዳዩን በአዎንታ ባያዩትም አዲሱ የሲአይኤ ዋና ዳይሬክተር ግን የትራምፕን ዕቅድ ለማስፈፀም የመጀመሪያው ሆነዋል።

አዲሱ የትራምፕ አስተዳደር ባሰበው ልክ ባይሆንም፤ አንዳንድ የፌደራል መንግሥት ሠራተኞች በፈቃዳቸው ሥራቸውን ሊለቁ ይችላሉ ተብሏል።

የሠራተኛ ማህበራት ኃላፊዎች ግን ሠራተኞች በፈቃዳቸው ሥራቸውን ለመልቀቅ እንዳይስማሙ አሳስበዋል ሲል ኤንቢሲ ዘግቧል።

Addis Admass

04 Feb, 20:55


የአዲስ አፍሪካ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን እና ኤግዚቢሽን ማዕከል በቀጣዩ ወር በይፋ ሊከፈት ነው

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሆነው የአዲስ አፍሪካ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን እና ኤግዚቢሽን ማዕከል በቀጣዩ ወር በይፋ እንደሚከፈት ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል ፡፡

ሚኒስቴሩ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባሰራጨው መረጃ አዲስ አበባ በየካቲት ወር ብቻ በርካታ አለም አቀፍ እና አህጉራዊ ኮንፈረንሶች ታስተናግዳለች ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሆነው የአዲስ አፍሪካ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን እና ኤግዚቢሽን ማዕከል (AAICEC) በይፋ እንደሚከፈትም አስታውቋል።

የማእከሉ መመረቅ በተለይ ለኮንፈረንስ ቱሪዝም (MICE) የበለጠ መነሳሳትን እንደሚፈጥር ተመልክቷል።

Addis Admass

03 Feb, 21:16


የዓለም ጤና ድርጅት የአሜሪካን ውሳኔ ለማስቀልበስ ሀገራት ጫና እንዲያደርጉ ጠየቀ
*********************
የዓለም ጤና ድርጅት የአሜሪካን ከድርጀቱ አባልነት የመውጣት ውሳኔ ለማስቀልበስ የሀገራት መንግስታት ጫና እንዲያደርጉ ጠይቋል፡፡
ድርጅቱ ባሳለፍነው ሳምንት ከዲፕሎማቶች ጋር በተካሄደ ዝግ ስብሰባ ላይ አሜሪካ ከአለም የጤና ድርጅት ለመውጣት ያስተላለፈችውን ውሳኔ እንድትቀይር ለሀገራት መሪዎች ጥሪ ማቅረቡም ነው የተገለፀው።
በስብሰባው ላይ የቀረበው የበጀት ሰነድ የዓለም ጤና ድርጅት የድንገተኛ አደጋ ፕሮግራም በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ ላይ ጥገኛ እደሆነ ያሳያል ተብሏል።
በስብሰባ ላይ የዓለም ጤና ድርጅት የፋይናንስ ዳይሬክተር ጆርጅ ኪሪያኩ ኤጀንሲው አሁን ባለበት መጠን ገንዘብ የሚያወጣ ከሆነ ድርጅቱ ከእጅ ወደ አፍ አይነት ሁኔታ ውስጥ ይሆናል ብለዋል።
አሁን ያለው የወጪ መጠን ከድርጅቱ የፋይናንስ አቅም አንፃር የማይቻል እየሆነ ስለመምጣቱም አክለዋል።
በተመሳሳይ የአሜሪካን ከአለም ጤና ድርጅት የመውጣት ውሳኔ ተከትሎ በዝግ ስብሰባው ላይ የተገኙት የጀርመን መልእክተኛ ቦሩን ኩመል “ጣሪያው እየተቃጠለ ነው፣ እና እሳቱን በተቻለ ፍጥነት ማቆም አለብን” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
በስብሰባው ላይ አሜሪካ ከአለም የጤና ድርጅት ከወጣች ስለ ዓለም አቀፍ የበሽታ ወረርሽኝ ወሳኝ መረጃዎችን እንደምታጣ ተመላክቷል።
በፈረንጆቹ ከ 2024-2025 ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ አሜሪካ ለዓለም ጤና ድርጅት ትልቁ ለጋሽ ሃገር ስትሆን 988 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ድጋፍ ማድረጓ ተጠቅሷል።
ይህ የአሜሪካ የገንዘብ ድጎማ የዓለም ጤና ድርጅትን 14 በመቶ የበጀት ድርሻ እንደሚሸፍን የዘገበው አሶሼትድ ፕረስ ነው።

Addis Admass

03 Feb, 21:04


በብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ የተመረጡ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት
1. ዐቢይ አሕመድ አሊ (ዶ/ር)
2. አቶ አደም ፋራህ
3. አቶ ተመስገን ጥሩነህ
4. አቶ ሽመልስ አብዲሳ
5. አቶ ከፍያለው ተፈራ
6. ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
7. አቶ አወሉ አብዲ
8. ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ
9. አቶ ፍቃዱ ተሰማ
10. አቶ ሳዳት ነሻ
11. ዶ/ር ተሾመ አዱኛ
12. ዶ/ር እዮብ ተካልኝ
13. አቶ ሙስጠፌ ሙሁመድ
14. አቶ አህመድ ሽዴ
15. ወ/ሮ ሀሊሞ ሀሰን
16. አቶ መላኩ አለበል
17. አቶ አረጋ ከበደ
18. አቶ ጃንጥራር አባይ
19. ዶ/ር አብዱ ሁሴን
20. ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ
21. አቶ ይርጋ ሲሳይ ቅጣው
22. ዶ/ር ሙሉነሽ ደሴ አድማሱ
23. አቶ ጥላሁን ከበደ
24. ዶ/ር ተስፋዬ በልጅጌ
25. ዶ/ር አበባየሁ ታደሰ
26. ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ
27. ዶ/ር እንደሻው ጣሰው
28. ወ/ሮ ሙፊሪሃት ካሚል
29. ዶ/ር ዲላሞ ኦቶሬ
30. ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ
31. አቶ ማስረሻ በላቸው
32. ሀጂ አወል አርባ
33. አቶ መሀመድ ሁሴን አሊሳ
34. አቶ መሀመድ አህመድ አሊ
35. አቶ ኦርዲን በድሪ
36. ወ/ሮ አሚና አብዱከሪም
37. ዶ/ር ፍፁም አሰፋ
38. አቶ ደስታ ሌዳሞ
39. አቶ አብርሃም ማርሻሎ
40.አቶ አሻድሊ ሀሰን
41. አቶ ጌታሁን አብዲሳ
42. ወ/ሮ አለሚቱ ኡሞድ
43. ዶ/ር ጋልዋክ ሮን
44. ዶ/ር አብርሃም በላይ
45. አቶ ታዜር ገ/ሔር

Addis Admass

03 Feb, 20:40


የዘመን ብርድ

(አሌክስ አብርሃም)

ፓብሎ ስኮባር ስለተባለ የአደንዛዢ እፅ ከበርቴ (Drug Lord ) ሰምታችኋል መቸስ። ከ1992- 93 የአሜሪካና ሜክሲኮ ኮማንዶዎች ሲያሳድዱት አምልጦ ብሩንና ልጁን በመያዝ የሜክሲኮ ቀዝቃዛ ተራራዎች ውስጥ ተደብቆ ነበር። ለአንድ ዓመት! ይሄ ሁሉ መከራ የመጣበት ያው ብር ለማግኘት በተዘፈቀበት ህገወጥ ስራ ነበር! እና በተደበቁበት ልጁ ብርዱን መቋቋም አልቻለችም። የሚሞቅ ነገር ፈለገ፣ ምንም የለም፤ ዞር ሲል የአሜሪካ ዶላር የታጨቀበት ሻንጣ አለ... መዘዝ እያደረገ ይለኩሰው ጀመር። ሲመዝ ሲለኩስ ፣ ሲመዝ ሲያነደው የሚወዳት ልጁን 2 ሚሊየን ዶላር አንድዶ ከቆፈን አወጣት!

በህይወት ውስጥ አንዳንዴ ክፉ ምርጫዎች ፊት ትቆማላችሁ፤ ለትንሽ ነገር ከብዙ በላይ የምትከፍሉበት ምርጫ! የዚህ ዘመን የኑሮ ብርድ ከማንዘፍዘፉ የተነሳ በብዙ ድካም፣ ያውም በንፁህ መንገድ ለዘመናት ያጠራቀምናቸውን ውድ እሴቶች ሁሉ አንድ በአንድ በመለኮስ እየሞቅናቸው ያለን ይመስለኛል። ፍቅር፣ ጓደኝነት፣ ሞራል፣ ሐይማኖት፣ ሰብአዊነት፣ ባህልና ወግ አገር ....ራሳችንን ጭምር! ማንን ለማዳን ይሆን?

Addis Admass

03 Feb, 20:37


ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትግርኛ ቋንቋ ለትግራይ ህዝብ ያስተላለፉት መልዕክት፤
(በአማርኛ የተተረጎመ፤ኤንቢሲ)

ምክር ለትግራይ ህዝብ በተለይም ለትግራይ ምሁራን!
…….
በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደገለጽኩት የትግራይ መሬትና ህዝብ የስልጣኔ መነሻ፤ የኢትዮጵያ ጋሻና መከታ ነው፡፡ የትግራይ መሬት የመንግስት አስተዳደር፣ የመንግስት ስርዓትና የሀገር እሴቶች የፈለቁበትና የተጠበቁበት ነው፡፡ የትግራይ ህዝብ ኢትዮጵያን በመፍጠርና ጠብቆ በማቆየት ውስጥ ያለው ሚና የማይካድ ሀቅ ነው፡፡ የትግራይ ህዝብ በማይፋቅ ቀለም የተፃፈ ብሩህ ታሪክ ያለው ህዝብ ብቻ አይደለም፤ ከምንም በላይ አገሩ ሀገሩን የሚወድ የሰላምና የብልጽግና ወዳጅ ብሎም ሥራ ወዳጅ የሆነ ህዝብ ነው፡፡ እንዲሁም በርካታ ህዝባቸውንና አገራቸውን የሚጠቅሙ ምሁራን፣ የሀይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞችና የሀገር ሽማግሌዎችን ያፈራ ህዝብ ነው፡፡

የትግራይ ህዝብ ከጥንት ጀምሮ የመንግስትን ምንነት ጠንቅቆ የሚያውቅና ከሌሎች ወንድሞቹ ጋር በመሆን ሀገረ መንግስትን የመሰረተ ህዝብ ጭምር ነው፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን ሀገረ መንግስት አደጋ ላይ በወደቀበት ወቅትም ከፍተኛ መስዋእትነት በመክፈል የኢትዮጵያን ሉአላዊነት ያስጠበቀ ማህበረሰብ ነው፡፡ ለዚህም ነው ከሌሎች ህዝቦች ጋር በመሆን ለሀገሩ ሉዓላዊነቱ ክብር ሲል ከድሩሽ፣ ከግብፅና ከጣሊያን፣ በኋላም ከምዕራብ ወይም ከምስራቅ እንዲሁም ከሰሜን ወራሪ ሃይሎች ጋር ተዋግቶ መስዋእትነት የከፈለው። በተጨማሪም ከሌሎች ወንድማማች ብሔሮች ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ልማት ውስጥ ትልቅ ሚና ተጫውቷል።

⬇️⬇️

Addis Admass

03 Feb, 20:37


ሌላው የትግራይ ህዝብ መለያ ለሀገሩ ያለው ፍቅር ነው፡፡ ልክ የትግራይ መሬት የኢትዮጵያ የስልጣኔ መሰረትና ማዕከል ሆኖ እንዳገለገለ ሁሉ፣ የትግራይ ህዝብ ልቡ በሀገር ፍቅር የተሞላ መሆኑ ታሪክን አጣቅሶ ለመመስከር መሞከር ለቀባሪው አረዱት እንደሚባለው ይሆናል፡፡ የትግራይ ህዝብ ሀገሩን በችግሩም ሆነ በሰላሙ ጊዜ ዋጋ እየከፈለ የአባቶቹን አደራ በመጠበቅ ማእከላዊው መንግስት በተለያዩ ዘመናት እንቅፋት ሲገጥመው ሀገሪቱን በማዳንና ክፍተቶችን በመሙላት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል።
ከአክሱማዊ መንግሥት ውድቀት በኋላ የተፈጠረውን ክፍተት በመዝጋት ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል። እንዲሁም በዘመነ መሳፍንት ጊዜ የነበሩ መከፋፈሎችን በማስተካከል፤ አገራዊ አንድነትን በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ ሚና ተጫውቷል።

የትግራይ ህዝብ ታታሪና ስራ ወዳድ ነው፡፡ የትግራይ ህዝብ ኮረብታ ላይ ወጥቶ ያርሳል፣ ድንጋይ ይቆርጣል፣ ፈልፍሎ ቤተመንግስት ይሰራል። ይህንን ግልጽ እና የታወቀ እውነታ ለማሳየት ማስረጃ ማቅረብ አያስፈልገኝም። የትግራይ ህዝብ ትንሽ ሰላም በነበረበት ወቅት በንግድ፣ በግብርና፣ በህንፃ፣ በኪነጥበብ፣ በቴክኖሎጂ መስክ ያከናወኗቸው ተግባራት ሁሉም የሚገነዘቡት ሃቅ ነው። ከዚህም በላይ በፈተና የማይናወጥ በመንፈስ የጠነከረ ሕዝብ ነው።

እንደ አለመታደል ሆኖ ግን በተለይ ባለፉት መቶ ዓመታት በተለያዩ አጋጣሚዎችና ምክንያቶች በተለይም ከማዕከላዊ መንግሥት ጋር በተፈጠረው ቅራኔ የትግራይ መሬት የጦር አውድማ ሆኗል፤ የትግራይ ሕዝብም የጦርነት ኢላማ ሆኗል። ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን መነሳት ያለበት ጥያቄ የትግራይ ህዝብ ባለፉት መቶ አመታት ጦርነት ምን አይነት ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም አገኘ፤ ምንስ አጠፋ የሚለው ነው፡፡

በዚህ ጊዜ አንድ አስተዋይ የትግራይ ምሁር ትግራይና ህዝቦቿ ከጦርነቱ የበለጠ ጥቅም አግኝተዋል ወይስ አጥተዋል ብሎ መጠየቅና መልስ ማግኘት አለበት። ሌላው ሊነሳ የሚገባው ጥያቄ፣ ጦርነቶች ሁሉ ብቸኛው አማራጭ ነበር ወይ? ሌላ መፍትሄ አልነበረውም? የሚለው ጥያቄ መልስ ነው። ከዚህ በኋላስ ጦርነትን ለመከላከል ምን የተሻለ ዘዴ መኖር አለበት የሚል ጥያቄ መጠየቅና መልሱን ማግኘት አስፈላጊ ነው፡፡

አሳዛኙ ነገር የትግራይ ህዝብ የትላንት ቁስሉ ሳያገግም ሰላም አግኝቶ ወደ መደበኛ ስራው እንዳይመለስ አሁንም በጦርነት ወሬ ፍርሃት ውስጥ እየኖረ ነው። እንዲህ ዓይነቱን አደጋ እንዴት መቋቋም እንደሚቻል ተረጋግቶ መወያየት ያለበት ጉዳይ መሆኑ ከጠቢባን የተሰወረ አይደለም። ስለዚህ የትግራይ ተወላጆች በፖለቲካ፣ በቢዝነስ፣ በደህንነት፣ በአካዳሚክና በሚዲያ ብሎም በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ ምሁራን እስካሁን የተከፈለው ዋጋ በቂ ነው፣ ከጦርነት ምንም ትርፍ የለም ፤ በመሆኑም በመካከላችሁ የተፈጠረውን አለመግባባት በሰላማዊና በተረጋጋ መንፈስ በመነጋገር፣ የትግራይን ህዝብ ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ እንድትፈቱት እጠይቃለሁ፡፡
በተጨማሪም ከፌዴራል መንግስትና ከሌሎች ሃይሎች ጋር ያላችሁን አለመግባባት በሀገሪቱ ህገ መንግስት መሰረትና በዲሞክራሲያዊ መንገድ ለመፍታት ዝግጁ እንድትሆኑ አሳስባለሁ። በፌዴራል መንግሥት በኩልም በሁሉም ጉዳዮች ላይ በመወያየት፣ የሃሳብ ልዩነቶችን እንደ የአመለካከት ልዩነት ወስዶ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ተስማምቶ ለመስራት ያለውን ፍላጎት በመረዳት ህዝቡን ከስቃይ፣ እናቶችን ከሰቆቃ፤ ወጣቶችን ከስደት ለማዳን እንድትሰሩ፤ በተለይ ደግሞ ህዝቡ ወደ ቀድሞ የልማት ስራው እንዲመለስ አብረን በድጋሚ እንድንሰራ እጠይቃለሁ፡፡

ሰላምና ብልፅግና ለትግራይ ህዝብ!

ጥላቻና ጦርነት ይብቃ!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ትኖራለች!!

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!

ጥር 26, 2017 ዓ.ም

Addis Admass

03 Feb, 20:24


38ኛውን የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ በላቀ ደረጃ ለማስተናገድ ዝግጅት መደረጉ ተገለጸ


በአዲስ አበባ ለሚካሄደው የዘንድሮ የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ እየተደረገ ያለውን ዝግጅት የተሳታፊ አገራት ቀዳሚ ልዑካን ቡድን አባላት የጎበኙ ሲሆን፤ኢትዮጵያ ስኬታማ ጉባኤን ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት ማድረጓን እንደተገነዘቡ በጉብኝቱ የተሳተፉ እንግዶች ገልጸዋል፡፡

የቡድኑ አባላት ብሔራዊ ቤተ መንግሥትን፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የክብር ሳሎንን፣ አዲስ አፍሪካ ኮንቬንሽን ሴንተርንና የአፍሪካ ሕብረት ዋና መሥሪያ ቤትን ተዘዋውረው መጎብኘታቸው ታውቋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄነራል አዚዛ ገለታ(ዶ/ር)፤ ጉብኝቱ ኢትዮጵያ ለጉባኤው እያደረገች ስላለው ዝግጅት ተሳታፊ አገራት በቂ መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

በጉብኝቱ የተሳተፉ እንግዶች ኢትዮጵያ ስኬታማ ጉባኤን ለማካሄድ የሚያስችል ዝግጅት ማድረጓን እንደተገነዘቡ መግለጻቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

Addis Admass

30 Jan, 20:18


የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች እስካሁን የ19 ሰዎችን አስከሬን ከወንዙ ማውጣታቸውን ገልፀዋል። 300 ገደማ የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች አደጋ በደረሰበት ሥፍራ አሰሳ በማካሄድ ላይ ናቸው።

በአካባቢው ባለው ከባድ ቅዝቃዜ ምክንያት የአደጋ ጊዜ ሥራው እጅግ አስቸጋሪ እንደሆ ተነግሯል። በአውሮፕላኑ ተሳፋሪ ከነበሩ ግለሰቦች መካከል ሁለት ሩሲያዊያን 'የስኬቲንግ' ስፖርተኞች እንደሚገኙበት ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።

ፖሊስ እና ጠላቂዎች በጀልባ ታግዘው ወንዝ ውስጥ ከአደጋው የተረፉ ሰዎች መኖራቸውን ለማጣራት አሰሳ እያካሄዱ ሲሆን የአሜሪካ ባለሥልጣናት የአደጋውን መንስዔ እየመረመሩ ይገኛሉ።

የፌዴራል አቪየሽን ባለሥልጣን እንዳለው አደጋው የተከሰተው በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 3፡00 ገደማ ሲሆን አውሮፕላኑ ሬገን ዋሺንግተን የሀገር ውስጥ አየር ማረፊያ ለማረፍ እየተቃረበ ነበር።

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ስለአደጋው ማብራሪያ እንደተሰጣቸው ገልፀው "መጥፎ አደጋ" ሲሉ ገልፀውታል።

የበረራ ቁጥሩ ፒኤስኤ ኤርላይንስ 5342 የሆነው ቦምባርዲዬር አውሮፕላን የአሜሪካ ጦር ንብረት ከሆነው ብላክ ሆክ ጋር መጋጨቱን አንድ ወታደራዊ ባለሥልጣን አረጋግጠዋል።

በቅርቡ የተሾሙት የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግሴዝ በሰጡት መግለጫ ፔንታገን ሁኔታውን "በተጠንቀቅ እየተከታተለ ነው" ብለዋል።

የአሜሪካ መገናኝ ብዙኃን እንደዘገቡት የአሜሪካን ኤርላይንስ ንብረት የሆነው አውሮፕላን በአደጋው ምክንያተ ለሁለት የተከፈለ ሲሆን ሄሊኮፕተሩ ደግሞ ተገልብጦ ወንዝ ላይ ተገኝቷል።

እስካሁን በአደጋው ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር በግልፅ ባይታወቅም የ19 ሰዎች አስከሬን ከወንዝ ወጥቷል። ነገር ግን በሥፍራው የነበሩ የዓይን እማኞችን አደጋው አየር ላይ ሲከሰት "ደማቅ ብርሀን" ማየታቸውን ኤንቢሲ ለተባለው ጣቢያ ተናግረዋል።

ሬገን አውሮፕላን ማረፊያ በአደጋው ምክንያት በረራ ማስተናገድ ያቆመ ሲሆን አውሮፕላኖች በአቅራቢያ ወደሚገኘው ዳለስ አየር መንገድ እንዲያቀኑ ተደርገዋል

Addis Admass

30 Jan, 20:18


በዋሺንግተን ዲሲ 60 ሰዎች የጫነ አውሮፕላን አየር ላይ ከጦር ሄሊኮፕተር ጋር ተጋጨ

አሜሪካን ኤርላይንስ የተሰኘው አየር መንገድ ንብረት የሆነ አውሮፕላን አየር ላይ ሳለ ከሄሊኮፕተር ጋር መጋጨቱን የፌዴራል አቪየሽን አስተዳደር አስታወቀ።

አውሮፕላኑ 60 መንገደኞች እና አራት የበረራ ሠራተኞች ጭኖ እንደነበር የታወቀ ሲሆን ሄሊኮፕተሩ ደግሞ ሶስት የአሜሪካ ወታደሮችን ጭኖ እንደነበር ተነግሯል።

የአውሮፕላን አደጋው የደረሰው ፖቶማክ የተባለ ወንዝ አቅራቢያ መሆኑን የዲሲ እሳት አደጋ መሥሪያ ቤት ገልጿል።

Addis Admass

30 Jan, 19:40


አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ 248 ሚ. ዶላር ብድር አጸደቀ

ዓለማቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ)፣ ሁለተኛውን የኢትዮጵያ የተራዘመ ብድር ግምገማ በማጠናቀቅ፣ ለአገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ ግብሩ፣ ትናንት ተጨማሪ 248 ሚሊዮን ዶላር ብድር ማጽደቁ ተነገረ፡፡

ድርጅቱ ለኢትዮጵያ 3. 4 ቢሊዮን ዶላር ብድር ባለፈው ሐምሌ ያጸደቀ ሲሆን፤ ከዚያ ወዲህ እስከ ትናንት ድረስ የለቀቀው ብድር 1.6 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ታውቋል፡፡ መንግሥት ለማኅበራዊ ሴፍቲ ኔት መርሃ ግብሮች የሚሰጠው ድጎማ ከተጠበቀው በታች መሆኑን የገመገመው ድርጅቱ፤ ለጉዳት ተጋላጭ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች የሴፍቲ ኔት ድጋፎችን ማጎልበት እንደሚያስፈልግ መክሯል።

ድርጅቱ፣ የነዳጅ ዋጋ የመንግሥትን ወጪ ሙሉ በሙሉ ሊመልስ በሚችል ደረጃ መስተካከል እንዳለበትም ምክረ ሃሳቡን አቅርቧል፡፡

Addis Admass

30 Jan, 19:38


“ኢትዮጵያ ተራማጅ ሀገር ናት”


አዲስ አበባ በአስደናቂ የለውጥ ጉዞ ላይ እንደምትገኝ መመልከታቸውን የሩዋንዳ ፓትሪዮቲክ ፍሮንት (አር ፒ ኤፍ) ፓርቲ ዋና ጸሃፊ ዌላርስ ጋሳማጌራ ገለጹ።

በነገው ዕለት አርብ በሚጀመረው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ለመታደም በመዲናዋ የሚገኙት ዌላርስ ጋሳማጌራ፤ የአንድነት ፓርክን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም አዲስ አበባ በለውጥ ጉዞ ላይ መሆኗን በአድናቆት የገለጹት ዋና ጸሃፊው፤ ኢትዮጵያ ተራማጅ ሀገር ናት ብለዋል።

የአንድነት ፓርክ የኢትዮጵያን ታሪካዊ ሀገርነት የሚገልጥ ብቻ ሳይሆን፣ ያለፈን ታሪክ ከዛሬ ጋር አስተሳስሮ በትንሽ ቦታ የሚያሳይ ድንቅ ስፍራ መሆኑንም ጋሳማጌራ ጠቁመዋል፡፡

Addis Admass

30 Jan, 19:36


የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
=====
አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx
ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv

Addis Admass

30 Jan, 19:32


በዚህ ረገድም እስካሁን ድረስ ከ60 በላይ ለሆኑ የልብ ህሙማን ሕፃናትና አዋቂዎች ያለክፍያ የልብ ቀዶ ሕክምና አገልግሎት መስጠቱን ጠቅሰዋል።

የህንድ ኦርቶዶክስ የፓትያርኩ ተወካይ በጉብኝቱ ወቅት ባዩት ሁሉ መደሰታቸውን ገልፀው፤ ከሆስፒታሉ ጋር በትብብር መሥራት የእነሱም ፍላጎት መሆኑን ተናግረዋል።

በአገራቸው ህንድ አራት ሆስፒታሎች ላይ በቦርድ አባልነትና ሊቀመንበርነት እንደሚያገለግሉ የገለጹት ተወካዩ፤ ኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታል ከእነዚህ ተቋማት ጋር አብሮ የሚሰራበትን ሁኔታ እንደሚያመቻቹ ጠቁመዋል፡፡ እዚህ የማይሰጡ ህክምናዎችን እሳቸው ከሚያስተባብሯቸው ሆስፒታሎች ጋር አብሮ እንዲሰራ በማድረግ፣ ድጋፍ እንዲያገኝ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንደሚያደርጉም ነው ቃል የገቡት፡፡

Addis Admass

30 Jan, 19:32


የህንድ የልዑካን ቡድን ኢትዮ ኢስታንቡል ሆስፒታልን ጎበኘ

• ሆስፒታሉ ከህንድ ሆስፒታሎች ጋር በትብብር ሊሰራ ነው

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቴዎስ ሣልሳዊ የህንድ ማላንካራ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ መልዕክተኛ፣ የልዑካን ቡድን፣ ሜትሮ ፖሊታን ማር ዩልዮስና ፋዘር ጆሲ ጃኮብ በዛሬው ዕለት ጠዋት ረፋድ ላይ የኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታልን ጎብኝተዋል፡፡

የኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃን ተድላ በጉብኝቱ መርሐ ግብር ወቅት ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፤ ከህንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጋር መቀራረቡ በተለይ ከፍተኛ ህክምናዎችን በሀገር ውስጥ ለማድረግ ሆስፒታሉ ያለውን ራዕይ ለማሳካት የሚረዳ ነው።

የኢትዮ-ኢስታንቡል ጠቅላላ ሆስፒታል፤በቴክኖሎጂ በታገዙ ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎችና ከፍተኛ ልምድ ባካበቱ ስፔሻሊስትና ሰብ-ስፔሻሊስት ባለሙያዎች በመታገዝ፣ ዜጎቻችንን ለህክምና ወደ ውጭ አገር በመጓዝ የሚያወጡትን ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪና እንግልት ለማስቀረት እንዲሁም ወደ ውጭ አገር የሚያስኬዱ ሕክምናዎችን በሀገር ውስጥ ለመስጠት አልሞ የሚንቀሳቀስ መሆኑ ተነግሯል፡፡

በዋናነትም ሆስፒታሉ በአዋቂና በህፃናት የልብ ቀዶ ህክምና ላይ የተሰማራ የሕክምና ተቋም ስለመኾኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አብራርተዋል። በተጨማሪም፣ የደረትና የሳንባ ቀዶ ጥገና ሕክምና፥ የጭንቅላትና ህብለሰረሰር ህክምና፥ የነርቭ ህክምና፥ የኩላሊት እጥበትና ህክምና፥ የአጥንት ቀዶ ሕክምና እና ጠቅላላ ህክምና ይሰጣል ተብሏል፡፡ ከዚህም ባሻገር ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለልብ ሕሙማን ህፃናት ያለ ክፍያ የቀዶ ህክምና በመስጠት የበኩሉን አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሚገኝ አቶ ብርሃን ገልፀዋል።

Addis Admass

30 Jan, 13:26


በደቡብ ሱዳን በደረሰ የአውሮፕላን አደጋ የሟቾች ቁጥር 20 መድረሱን ፕሬዚዳንቱ አስታወቁ

ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር በሰጡት መግለጫ "ይህ ልብ የሚነካ ክስተት የ 20 ንፁሃን ሰዎች ሕይወትን ቀጥፏል፣ አንድ ሰው ተርፏል" ብለዋል።

ረቡዕ ዕለት 21 ተሳፋሪዎችን ያሳፈረ አውሮፕላን በሰሜናዊው የአገሪቱ ክፍል ከሚገኘው የአንድነት የነዳጅ ማደያ ሲነሳ የመከስከስ አደጋ አጋጥሞታል።

ፕሬዝዳንቱ የትራንስፖርት ሚኒስቴር እና ሁሉም የሚመለከታቸው ባለስልጣናት የአደጋውን መንስኤ ለመለየት ጥልቅ እና ፈጣን ምርመራ እንዲያካሂዱ መመሪያ መስጠታቸውን መግለጫው አመልክቷል።

Addis Admass

30 Jan, 13:20


ሆኖም ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸው ተጠቅሷል።
በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።
የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ወንጀሉ የተፈጸመው በትብብር መሆኑን ጠቅሶ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ ይዟል።
በዚህም1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን ያቀረቡትን አራት የቅጣት ማቅለያ በመያዝ በዕርከን 21 መሰረት በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።
2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ እያንዳንዳቸው አራት፣ አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት በመያዝ በዕርከን 17 መሰረት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።
በፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የተወሰነውን የጽኑ እስራት ውሳኔን የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እጃቸው ከተያዘ ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ እንዲያስፈጽም ታዟል።

Addis Admass

30 Jan, 13:20


ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ
የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።
በዚህም ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።
በዚህ መልኩ የቀረበውን ዝርዝር ክስ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።
ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።
ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።
ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቶ ነበር።
ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት በሐሰተኛ ሰነድ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑ በአንደኛውን ክስ ላይ መገለጹን ተከትሎ በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው በተደራራቢነት የቀረቡና ተጠቃልለው ሊያስቀጡ የሚችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ፍርድ ቤቱ አብራርቶ ሁለተኛውን ክስ ውድቅ በማድረግ በአንደኛው ክስ ብቻ በከባድ አታላይነት ሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

Addis Admass

29 Jan, 20:23


ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመት በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ነው

በቀጣይ ዓመት ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆን በዝግጅት ላይ ነው



ጎንደር ዩኒቨርሲቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመትና የማስተማሪያ አጠቃላይ ሆስፒታሉን የመቶኛ ዓመት ምስረታ በዓል በተለያዩ መርሃ ግብሮች ማክበር ጀምሯል። ባለፈው ረቡዕ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) በተገኙበት በይፋ የተከፈተው ክብረ በዓል፤ እስከ ሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም በተለያዩ ዝግጅቶች እንደሚከበር የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው ገልጸዋል።
በ1942 ዓ.ም ኢትዮጵያ የጤና ሰራተኞች እንደሚያስፈልጋትና የጤና አጠባበቅ ትምህርት የሚቀስሙበት ማሰልጠኛ ተቋም እንዲከፈት የዓለም የጤና ድርጅት ማሳሰቡን ተከትሎ ነው የጎንደር ጤና ማሰልጠኛ ጣቢያ የተቋቋመው፡፡ በወቅቱ ኢትዮጵያዊያን የጤና ባለሙያዎች ስላልነበሩ ወጣቶች እየተመረጡ ውጪ ሐገር እንዲሰለጥኑና የጤና አጠባበቅ ሰራተኞች በሃገር ውስጥ የሚሰለጥኑበት ተቋም እንዲመሰረት የተወሰነ ሲሆን፤ መስከረም 24 ቀን በ1947 ዓ.ም የጎንደር ጤና አጠባበቅ ኮሌጅ ከሐሳብ ወደተግባር መቀየሩን የዩኒቨርሲቲው ታሪክ ይጠቁማል፡፡
ምስረታው እውን እንዲሆን የኢትዮጵያ መንግሥት፣ የዓለም የጤና ድርጅትና የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የተራድኦ ድርጅት የተባበሩ ሲሆን፤ በወቅቱ “የጎንደር ጤና ማሰልጠኛ ጣቢያ” በሚል ስያሜ መቋቋሙ ተገልጿል። በዚሁ የምስረታው ዓመት በአገር ግዛት ሚኒስቴር ስር አንድ ዘርፍ ይዞ የነበረው የህዝብ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር በመባል ከፍ ባለ ደረጃ እንዲመራ በነጋሪት ጋዜጣ አዋጅ ቁጥር 91 መታወጁን የሚያትተው የዩኒቨርሲቲው ታሪክ፤ በ1948 ዓ.ም ደግሞ በሐገሪቱ የሚካሄደው ማንኛውም የጤና ትምህርት በሕዝብ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ስር እንዲተዳደር በመታዘዙ፣ ይህ የማሰልጠኛ ተቋምም በሚኒስቴሩ አመራር ስር እንዲውል መደረጉ ተመልክቷል። ማሰልጠን ከመጀመሩ በፊትም፣ የጤና ማሰልጠኛ ጣቢያ የሚል ስያሜውን በ1947 ዓ.ም ስራውን ሲጀምር፣ የጎንደር ህዝብ ጤና ጥበቃ ኮሌጅና ማሰልጠኛ ወደሚል ቀየረ። ከዚህ በኋላ ብዙ ሂደቶችን ያለፈው ኮሌጁ፤ ከጤና ዘርፍ ውጪ በርካታ የትምህርት ዘርፎችን አካትቶ፣ በ1996 ዓ.ም ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ወደሚል ስያሜ መሸጋገሩን ፕሬዚዳንቱ አስራት አፀደወይን (ዶ/ር) አብራርተዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ

https://t.ly/t7qnz

Addis Admass

29 Jan, 20:22


እኔ ወይስ ሌላኛው እኔ?

በአብርሀም ገነት

ይሄ ገጠመኝ መቼቱ አይታወቅም፡፡ ገጠመኙ የሆነ የተፈፀመ ነው፣ የት እና መቼ እንደተፈፀመ ግን አይታወቅም፡፡ ታሪኩ ተራ የሚመስል ገጠመኝ ነው፣ በልቦናዬ የፈጠረው ጥልቀት ግን መለኪያ የለውም፡፡ ታሪኩ አጭር ነው፣ የታሪኩን ዳና ግን ሁለንታውን በጠቅላላ ባስስ እንኳን የምደርስበት አይመስለኝም፡፡ ቀን ላይ የተፈጠረ ገጠመኝ እንደሆነ ግን አውቃለሁ፣ ምክንያቱም የልጅቷን ብሩህ ፈገግታ አይቼዋለሁ፡፡
እንዲህ ነበር….
ሱሪዬን አውርጄ መፀዳጃ ቤት ውስጥ ተቀምጫለሁ፡፡ የመፀዳዳት ተግባር እርካታ እንደሚሰጥ ሁላችንም እናውቃለን፤ እናም በዚህ እርካታ ታጅቤ፣ በሌላ ሀሳብ ውስጥ ሰምጬ የት እንደተቀመጥኩ እንኳን ረስቻለሁ፡፡ የት እንዳለሁ ብቻ ሳይሆን ምን እያደረግሁ እንደነበረም ረስቻለሁ፡፡ ጨርሼ ልታጠብ እጄ በልማዱ መሰረት ውሃ ፍለጋ ሲያማትር፣ ልቦናዬ ወደ ተጨባጭ ከባቢዬ ተመለሰ፡፡ ከተወሰድኩበት የሀሳብ አለም ስመለስ የት እንዳለሁ አወቅሁ፣ መፀዳጃ ቤት ውስጥ ተቀምጬ ነው ያለሁት፡፡ ቀና ስል መፀዳጃ ቤቱ ክፍት ነው፡፡ በሩን ወርውሬ ለመዝጋት በተቀመጥኩበት ስንጠራራ መፀዳጃ ቤቱ በር የለውም፡፡ ደንግጬ ሰው ሳያየኝ ቶሎ ከጉልበቴ በታች ያለ የውስጥ ሱሪዬንና ሱሪዬን እየታጠቅሁ ልቆም ስል ሱሪ የለኝም፡፡ እየተጣደፍሁ ሀፍረቴን በውስጥ ሱሪዬ ልሸፍን እጄን ስሰድ የውስጥ ሱሪም የለኝም፡፡ ፊት ለፊቴ ሳይ ወደ መፀዳጃ ቤቱ ልትገባ ወረፋ ስትጠብቅ የነበረች ልጅ ቆማ እያየችኝ ነው፡፡ ደነገጥኩ፡፡ አፈርኩ፡፡ በደመነፍስ እጆቼን ጭኖቼ መሀል አደረኩ፡፡ ልጅቷ ቅንነት ከተሞላበት የሚያፅናና ፈገግታ ጋር “አይዞህ ፓንት የለኝም ብለህ አትፈር፣ እንትን የሌለው አለና” አለቺኝ፡፡ ከዚያ “ቆይ ፎጣ ላምጣልህ” ብላ ወደ ቤቷ ፈጠነች፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ
https://t.ly/7i4qf

Addis Admass

29 Jan, 20:01


የኢትዮጵያ ኢስላማዊ ምሁራን የአንድነት ጥሪ
ከተሾመ ብርሃኑ ከማል

ኢትዮጵያ በእስልምና ታሪክ ውስጥ ልዩ እና ወሳኝ ቦታ አላት። ከመካ ስደት ለሚሸሹ የጥንት ሙስሊሞች የመጀመሪያ መሸሸጊያ ቦታ በመባል የምትታወቀው ሀገሪቱ፣ ከእምነቱ አመጣጥ ጋር የተሳሰረ ነው። እ.ኤ.አ በ615፣ በነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) የሕይወት ዘመን፣ አንዳንድ የቅርብ ጓደኞቻቸውን ጨምሮ የጥንት ሙስሊሞች ቡድን በአቢሲኒያ (በዛሬይቱ ኢትዮጵያ) መሰደድን ፈለጉ። ክርስቲያኑ ንጉሠ ነገሥት (አስሐማ ኢብኑ አብጀር) አቀባበልና ጥበቃ አደረገላቸው፡፡ በእምነታቸውና በጋራ የፍትህ እና የሰላም እሴት መሰረት ጥገኝነት ሰጣቸው። ይህ ክስተት በእስልምና ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን የሂጅራ (የስደት) ጉዞን ያስመዘገበ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ እና በሙስሊሙ ዓለም መካከል ዘላቂ ትስስር ፈጥሯል።
ዛሬ ኢትዮጵያ 50 ሚሊዮን የሚገመቱ እስልምና እምነት የሚከተሉ አማኞች ካሏቸው የአፍሪካ አገራት አንዷ ናት። እስልምና ለዘመናት የሀገሪቷ ባህላዊ፣ ማህበራዊና ሃይማኖታዊ መዋቅር ዋነኛ አካል ሲሆን፤ ለብዝሀነቷና ለቅርሶቿ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክቷል። ይህ ታሪካዊ ፋይዳ እና የሙስሊም ህዝቦቿ መብዛት እንዳለ ሆኖ የኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብ ምሁራዊ አስተዋፅዖ ካለው እምቅ አቅም እና በጣም ትንሽ ህዝብ ባለባቸው ሀገራት ካስመዘገቡት የእስልምና ምሁር ውጤቶች አንፃር ሲታይ አነስተኛ ነው።

ይህም ሆኖ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ እውቅና ያላቸው የሙስሊም ምሁራን ቁጥር እጅግ በጣም አናሳ ነው፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩ ታዋቂ ግለሰቦች ቢኖሩ ከነሱም ውስጥ የህግ አስተያየት የሚሰጡ ሙፍቲዎች እና ከፍተኛ የእስልምና ሊቃውንት የሚባሉት ከአስር ቤት የሚበልጡ አይደሉም፡፡ ከነዚህ ምሁራን መካከል ኢስላማዊ መጽሕፍትን ያሳተሙት በጣት የሚቆጠሩ ብቻ ሲሆኑ፤ ከአስር የማይበልጡ ደራሲያን ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሥራዎችን እንደሠሩ ይገመታል። እስካሁን ድረስ አንድም ኢትዮጵያዊ የእስልምና ምሁር ከ100 በላይ መጻሕፍት እንደፃፈ አይታወቅም፡፡ በትርጉም ሥራም ቢሆን ብዙ ሠርተዋል የሚባሉት ምሁራን ከአንድ ቤት የሚዘሉ አይደሉም፡፡

ይህ ንፅፅር ከ10 ሚሊዮን ያነሱ ሙስሊሞች ካላቸው ሀገራት ጋር ሲወዳደር የበለጠ ጎልቶ ይታያል። በእንደዚህ ያሉ ሃገራት ውስጥ በሺዎች የሚቆጠሩ ምሁራን እና የሃይማኖት መሪዎች በመቶዎች የሚቆጠሩ መጻሕፍትን በመጻፍ እና የነቃ ምሁራዊ ስነ-ምህዳርን በመቅረጽ ለኢስላማዊ ስነ-ጽሁፍ ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክተዋል።
ለምሳሌ፣ አገሪቱ ጥቂት መቶ ያህል እውቅና ያላቸው የሙስሊም ምሁራን ያሏት ሲሆን የሙፍቲዎች ብዛት- ማለትም የህግ አስተያየት እንዲሰጡ የሚፈቀድላቸው ከፍተኛ የእስልምና ሊቃውንት- በአንድ ቤት የሚቆጠሩ ናቸው። ችግሩን ከኢስላማዊ ስነጽሑፍ አኳያ ስንመለከተው ልዩነቱ አስደንጋጭ ነው። ካሉት ከፍተኛ ምሁራን መካከል፣ በአስር ቤት የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሙስሊም ምሁራን ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ኢስላማዊ መጻሕፍትን ጽፈው ይሆናል። እስካሁን ድረስ፣ ከ100 በላይ የራሱ የሆኑ ሥራዎችን ያሳተመ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ምሁር ስለመኖሩ አይታወቅም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

https://t.ly/5PU9W

Addis Admass

29 Jan, 19:46


https://t.ly/BX6nX

Addis Admass

29 Jan, 19:34


ማይክሮሶፍት ቲክቶክን ሊገዛ እየተደራደረ ነው ተባለ


• ሌሎች የአሜሪካ ኩባንያዎችም ፍላጎት አሳይተዋል


የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ማይክሮሶፍት ኩባንያ፣ ቲክቶክን ለመግዛት በውይይት ላይ መሆኑንና በማህበራዊ ሚዲያው ሽያጭ ላይ የሚደረጉ ፉክክሮችን ማየት እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡

ግዙፉ የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ማይክሮሶፍት፣ ለጨረታ ዝግጁ ስለመሆኑ የተጠየቁት ፕሬዚዳንቱ፤ “አዎን” በሚል ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ በርካታ ኩባንያዎችም ቲክቶክን ለመግዛት ከፍተኛ ፍላጎት ማሳየታቸውን ተናግረዋል፡፡

ትራምፕም ሆኑ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን፣ ከብሔራዊ ደህንነት ስጋት ጋር በተያያዘ የቻይናው ኩባንያ ቲክቶክ እንዲሸጥ ለዓመታት ግፊት ሲያደርጉ መቆየታቸው አይዘነጋም፡፡

በአሜሪካ 170 ሚሊየን ተጠቃሚዎች ያሉት ቲክቶክ መተግበሪያ እንዲታገድ ባለፈው ሳምንት የባይደን አስተዳደር ያሳለፈውን ውሳኔ ፕሬዚዳንት ትራምፕ ለ75 ቀናት እንዲራዘም ማዘዛቸው ይታወቃል፡፡

Addis Admass

29 Jan, 19:03


“ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” የግጥም መድበል አርብ ይመረቃል

በገጣሚት መሠረት አዛገ “ሺ ጊዜ እንዳፈቅር” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው የግጥም መድበል፣ ከነገ ወዲያ አርብ 4 ኪሎ በሚገኘው ዋልያ መጻሕፍት፣ አንጋፋ የኪነጥበብ ሰዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሥነጽሑፍ ቤተሰቦች በተገኙበት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡

በምረቃው ሥነስርዓት ላይ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ አያልነህ ሙላቱ፣ ጸሐፌ ተውኔትና ገጣሚ ሥዩም ተፈራ፣ ደራሲና ጋዜጠኛ ዘነበ ወላ፣ ደራሲና መምህር ኃ/መለኮት መዋዕል፣ መምህር የሻው ተሰማ (የኮተቤው) እና ወጣት ገጣሚያን ሥራቸውን ያቀርባሉ፡፡

ገጣሚ መሠረት አዛገ፣ የ”መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት” መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ስትሆን፣ ላለፉት 14 ዓመታት በህጻናትና በእናቶች ድጋፍና እገዛ ላይ በሠራቻቸው ሥራዎች በርካታ ሽልማቶችን ከሀገር ውስጥና ከተለያዩ የውጪ ሀገራት እንዲሁም ዓለም አቀፍ ተቋማት ማግኘት የቻለች እንስት ናት፡፡

Addis Admass

29 Jan, 19:02


በደቡብ ጎንደር ዞን እስቴ ዴንሳ ከተራራው ስር በዓለ መርቆሬዎስ እንዲህ አምሮ እና ደምቆ ይነግሳል።

Addis Admass

29 Jan, 19:01


የመቀለ ኤፍኤም ሬዲዮ ጣቢያን በኃይል ለመቆጣጠር
የተደረገው ሙከራ መክሸፉ ተነገረ


በትግራይ ክልል በህወሓት አመራሮች መካከል ያለውን ክፍፍልና አለመግባባት ተከትሎ፣ አንድ የፓርቲው አባል በአምስት ታጣቂዎች በመታገዝ፣ በዋና ከተማዋ መቀለ የሚገኝ ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያን ለመቆጣጠር ባደረገው ሙከራ፣ ለሰዓታት የዘለቀ ውዝግብ መከሰቱን የጣቢያው ሠራተኞችና ፖሊስ ለቢቢሲ አረጋገጡ።

በዛሬው ዕለት ጥር 21 ቀን 2017 ዓ.ም. ረፋድ ላይ አንድ የፀጥታ ኃላፊና አምስት ታጣቂዎችን ይዞ ወደ መቀለ 104.4 ኤፍ ኤም ጣቢያ የደረሰው ግለሰብ፤ ጣቢያውን ለመቆጣጠር ያደረገው ጥረት መክሸፉን የጣቢያው ሠራተኞች ተናግረዋል።

ከአምስት ታጣቂዎች ጋር ወደ ጣቢያው ያመራው ግለሰብ፣ ዘመንፈስቅዱስ ፍሰሃ የሚባል የህወሓት አባል ሲሆን፤ ጣቢያውን ለማስተዳደር በመቀለ ከተማ ምክትል ከንቲባ ዶ/ር ረዳኢ "ተሹሚያለሁ" ሲል መናገሩ ተገልጿል። ዶ/ር ረዳኢ በዶ/ር ደብረጽዮን በሚመራው የህወሓት ክንፍ ለመቀለ ከንቲባነት የተሾሙ ሲሆን፤ በክልሉ ጊዜያዊው አስተዳደር ግን ሕገወጥ ከንቲባ ተደርገው ይወሰዳሉ።

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አንድ የሬዲዮ ጣቢያው ሠራተኛ፤ አቶ ዘመንፈስቅዱስ ፍሰሃ የተባለው ግለሰብ በታጣቂዎች ታግዞ ወደ ጣቢያው ከዘለቀ በኋላ የተቋሙን ማህተም ከፀሐፊዋ በመንጠቅ ለሠራተኞች ማስታወቂያ መለጠፉን ተናግረዋል።

ስለ ክስተቱ ለቢቢሲ የተናገረ ሌላ የጣቢያው ሠራተኛ ደግሞ በዶ/ር ደብረጽዮን በሚመራው የህወሓት ክንፍ ደጋፊ የሆነ ግለሰብ፣ ደብዳቤ እንኳ ሳይዝ ጣቢያውን በኃይል ለመቆጣጠር ሙከራ ማድረጉን አረጋግጧል።

⬇️⬇️

Addis Admass

29 Jan, 19:01


ይህ ግለሰብ እንደሚለው፤ ይህ ክስተት በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው ኃይል የትግራይ ቴሌቪዥንና ድምጸ ወያኔ የብዙኃን መገናኛ ተቋማት ከእጁ ስለወጣ ኤፍ ኤም መቀለን በመሣሪያ ኃይል በመንጠቅ መጠቀሚያ ለማድረግ ያደረገው ሙከራ ነው።

ሌላ የድርጅቱ ሠራተኛ በበኩሉ፤ አቶ ዘመንፈስቅዱስ ፍሰሃ "በዶክተር ረዳኢ የተሾምኩት ትክክለኛው የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ እኔ ነኝ፣ ሥልጣን አስረክበኝ" በሚል ነባር የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ሀለፎም ንርአን እንደጠየቀ ተናግሯል።

"ሥልጣን አስረክበኝ አለው፣ አቶ ሀለፎም ደግሞ ሹመት የሰጠህ ዶ/ር ረዳኢ በጊዜያዊ አስተዳደሩ ሕገወጥ የተባለ ሰው ስለሆነ ሥልጣን ላስረክብህ አልችልም። ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ደብዳቤ ይዘህ ከመጣህ ግን ሥልጣን አስረክብሃለው አለው፤ በዚህን ጊዜ አቶ ዘመንፈስ ቅዱስ ማኅተብ ከፀሐፊዋ በኃይል አስገድዶ ወስዶ፣ ለጣቢያው ሠራተኞች የስብሰባ ጥሪ ማስታወቂያ ለጠፈ" ብሏል።

ይህን ተከትሎ አቶ ሐለፎም፤ "እኔ እያለሁ ለምን ማህተም ነጥቀህ ማስታወቂያ ትለጥፋለህ?” በማለት የተለጠፈውን ማስታወቂያ እንዳነሱትና በዚህም የተነሳ ውጥረት እንደተፈጠረ ተናግሯል።

ይህ ፍጥጫ ከጠዋቱ 3፡30 እስከ ቀትር 6፡00 ሰዓት የቆየ ሲሆን፣ በመጨረሻ ከቀዳማዊ ወያነ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ተጠርቶ ሁለቱንም ግለሰቦችና ጣቢያውን ለመቆጣጠር የመጡትን ታጣቂዎች ይዘዋቸው መሄዳቸውን የጣቢያው ሠራተኞች ለቢቢሲ አረጋግጠዋል።

በአሁኑ ሰዓት መቀለ በሁለቱም ህወሓት ክንፎች የተሰየሙ ከንቲባዎች ቢኖሯትም ላለፉት ሦስት ወራት ያለ ከንቲባ ቆይታለች። ቢቢሲ የዛሬ ጠዋቱን ከስተት በተመለከተ ለጣቢያው ነባር ሥራ አስኪያጅ አቶ ኃለፎም እንዲሁም ተሾሚያለሁ ለሚሉት አቶ ዘመንፈስቅዱስ ስልክ ደውሎ ለማነጋገር ያደረገው ሙከራ አልሰመረም።

ቢቢሲ ያነጋገራቸው የመቀለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ኮማንደር አንድነት ነገሰ በበኩላቸው ጣቢያውን ለመቆጣጠር የተደረገውን ሙከራ አረጋግጠው ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል።

ኤፍ ኤም መቀለ 104.4 ጣቢያ፤ በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለሥልጣን ሕግ መሠረት በትግራይ ክልል ቴሌቪዥን ፈቃድ የሚንቀሳቀስ ሆኖ ከተመሠረተ 16 ዓመታት ያስቆጠረ የሬዲዮ ጣቢያ ነው።

Addis Admass

20 Jan, 21:11


ዶናልድ ትራምፕ ባደረጉት ንግግር የቀድሞውን ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና ምክትላቸውን ካማላ ሐሪስ አስመልክተው "የአሜሪካ ወርቃማ ዘመን አሁን ይጀምራል" ብለዋል።

"ከዚህ ቀን በኋላ አገራችን ታድጋለች፣ ትከበራለች፣ አሜሪካ ትቀድማለች" ብለዋል።

ትራምፕ በዓለ ሲመታቸው በሚከናወንበት የካፒቶል ሂል አዳራሽ አካባቢ በደጋፊዎቻቸው ተሞልቷል። ከዜሮ በታች 5 ዲግሪ ሴንቲ ግሬድ ቅዝቃዜ ቢኖርም የትራምፕን ንግግር ለመስማት ደጋፊዎቻቸው ተሰባስበዋል።

ከትራምፕ ደጋፊዎች አንዷ "የቤተሰብ ዋጋ የሚጠበቅባቸው" እርምጃዎች ይወሰዳሉ ብላ እንደምትጠብቅ ተናግራለች። የቀድሞው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን እና የትራምፕ ተፎካካሪ የነበሩት ምክትላቸው ካማላ ሀሪስ ወደ አዳራሹ ሲገቡ ጭብጨባ ተደርጎላቸዋል
ትራምፕ ቃለ መሐላ ሲፈጽሙ ለአሜሪካ ያላቸውን የወደፊት ዕቅዶች ተናግረዋል።

"ሉዓላዊነታችንን መልሰን እናስከብራለን። ደኅንነታችን የተጠበቀ ይሆናል። የተዛባው ፍትሕ ይሰፍናል" ብለዋል።

"ዋና ግባችን ኩሩ አገር መገንባት ነው። ኩሩ፣ ነጻና የበለጸገች" ሲሉም አክለዋል።

Addis Admass

20 Jan, 20:53


በእስራኤል የቤተሰብ ጉዳይ ፍርድ ቤት ርእሾን ለፂዮን
የፋ/ቁጥር 18766-10-24
በተከበሩ ዳኛ ሃጊት ማጣሊን ም/ፕሬዚዳንት ፊት፡፡
ተከሳሽ አቶ ኤርሚያስ አዱኛ ጂማ ISRA መ/ቁ 342470309 አድራሻ:-
ቦሌ ወረዳ 3 የቤት ቁጥር 918፤ አዲስ አበባ ኢትዮጵያ፡፡
ከሳሽ ወ/ሮ ታከለ ቢሊን ISRA መ/ቁ 328819628 አድራሻ፡-
ዛልማን ሽኔ ኦር ጎዳና 20/14 ርእሾን ለፂዮን እስራኤል፡፡
ተከሳሽ፤ ለቀረበብዎት የፍች ክስ፣ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን
ጀምሮ በ45 ቀናት ውስጥ ርእሾን ለፂዮን ለሚገኘው የቤ/ጉ/ፍ/ቤት መልስ
እንዲሰጡ ወይም መከላከያ ያቀርቡ ዘንድ በ1948 ዓ.ም በወጣው
አንቀፅ ለ 1 ህግ መሰረት ይገደዳሉ፡፡
አቪ ቢተው የከሳሽ የህግ ጠበቃ፣ ናሁም ሶኮሎቭ ጎዳና ቁጥር 11፣
ኮድ 7220529 ራምሌ እስራኤል፡፡
ስ/ቁ +972-8-9222497 ፋክስ ቁ +972-8-9222956

Addis Admass

20 Jan, 20:40


ትራምፕ ቃለ መሐላ መፈጸማቸውን ተከትሎ ስደተኞችን ማባረር እና ግዛት ማስፋፋትን ተግባራዊ እንደሚያደርጉ ተናገሩ በአሜሪካ ባለፈው ኅዳር ወር የተካሄደውን ምርጫ ያሸነፉት ዶናልድ ትራምፕ ዋሺንግተን ውስጥ በተካሄደ ሥነ ሥርዓት ቃለ መሐላ ፈጽመው የፕሬዝዳንትነት ሥልጣኑን ተረከቡ።

ትራምፕ ከአራት ዓመት በፊት 45ኛ ፕሬዝዳንት ሆነው አሜሪካን ከመሩ በኋላ በጆ ባይደን ተሸንፈው ከመንበራቸው ተሰናብተው ከቆዩ በኋላ ነው በአስደናቂ ሁኔታ በድጋሚ ተመርጠው ለሁለተኛ እና ለመጨረሻ ዙር የሥልጣን ዘመን ወደ ሥልጣን የተመለሱት።

በከፍተኛ ቅዝቃዜ ምክንያት በዋይት ሐውስ ውስጥ የተወሰኑ ተጋባዦች በተገኙበት በተካሄደው ሲመተ በዓል ላይ ዶናልድ ትራምፕ እና ጄዲ ቫንስ ፕሬዝዳንት እና ምክትል ፕሬዝዳንት ሆነው ቃለ መሐላቸውን ፈጽመዋል።

Addis Admass

20 Jan, 20:40


ሰኞ ጥር 12/2017 ዓ.ም. በዋሽንግተን ሰዓት አቆጣጠር እኩለ ቀን ላይ በተካሄደው የፕሬዝዳንት ሲመተ በዓል ላይ የቀድሞዎቹ የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች ቢል ክሊንተን፣ ዶርጅ ደብሊው ቡሽ፣ ባራክ ኦባማ እና ተሰናባቹ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ታድመዋል።

የቀድሞው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን እና የትራምፕ ተፎካካሪ የነበሩት ምክትላቸው ካማላ ሐሪስ ወደ አዳራሹ ሲገቡ ጭብጨባ ተደርጎላቸዋል።

የትራምፕ የቅርብ አጋሮች የሆኑት ቢልየነሮቹ ሊላን መስክ፣ ጄፍ ቤዞስ፣ ማርክ ዙከርበርግ፣ ሰንደር ፒቺ እና ሎውረን ሳንቼዝም በዓለ ሲመቱን ታድመዋል።

ትራምፕ በሜክሲኮ ድንበር አቅራቢያ "ብሔራዊ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ" ያወጁ ሲሆን፣ ወደ አሜሪካ "በሕገ ወጥ መንገድ መግባት ይቆማል" ብለዋል።

ትራምፕ በመጀመሪያው ንግግራቸው ቀደም ሲል ሲናገሩት እንደነበረው በአሜሪካ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ሕገወጥ ስደተኞች ከአገሪቱ እንደሚያናርሩ ገልጸዋል።

በተጨማሪም የፓናማ ካናልን መልሰው በአመሪካ ቁጥጥር ሥር እንሚያስገቡ እንዲሁም፣ የአገራቸው ሰንደቅ ዓላማ በማርስ ላይ እንደሚውለበለብ አመልክተዋል።

በተጨማሪም በእሳቸው የአስተዳደር ዘመን በአሜሪካ ውስጥ ዕውቅና የሚኖራቸው ሁለት ፆታዎች እነሱም ወንድ እና ሴት ብቻ እንደሚሆኑ ተናግረዋል።

"ወንጀለኛ መጤዎች ወደ መጡበት ይመለሳሉ" ሲሉም ትራምፕ ተደምጠዋል።

ትራምፕ በተጨማሪም አደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎችን "አሸባሪ" ብለው ፈርጀዋል።

ትራምፕ ምጣኔ ሀብተን፣ ሕግን፣ ዓለም አቀፍ ግንኙነትን እና ሌሎችንም ቁልፍ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርገው ሲናገሩ ከታዳሚው ሞቅ ጭብጨባ ተለግሷቸዋል።

Addis Admass

20 Jan, 20:13


በትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ
በክልተ ኣውላዕሎ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
አደጋው ከሓውዜን ወደ መቐለ ሲጓዝ የነበረ ሚኒባስ በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚጓዝ ቅጥቅጥ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ጋር በመጋጨቱ ነው የተከሰተው፡፡
በአደጋው ከሟቾች በተጨማሪ ስድስት ሰዎች ላይ ከባድ ጉዳት መድረሱን የወረዳው ፖሊስ መረጃ ያመላክታል፡፡(ኤፍ ኤም ሲ)

Addis Admass

18 Jan, 21:41


መልካም የጥምቀት በዓል

Addis Admass

18 Jan, 20:07


በጎንደር የጥምቀት በዓል ዋዜማ የከተራ ሥነ ሥርዓት እየተካሄደ ነው።

Addis Admass

17 Jan, 21:45


ከአዲስ አድማስ ጋር ከተዋወቅሁ ጊዜው ቆየ፡፡.ማስታወስ አልቻልኩም....እማውቀው ከጥንት እስካሁን ድንቅ ጋዜጣ መሆኗን ነው...

(ደራሲና ገጣሚ ታገል ሰይፉ)

Addis Admass

17 Jan, 20:17


ከድሮም ጀምሮ አነብ ነበር፣ ይሁንና ከዕለታት አንድ ቀን ለስራ ጉዳይ ጅማ ከተማ ሄድኩኝ፣ በከተማዋ ውስጥ ስዘዋወር ጋዜጣ የሚያዞር ልጅ አየሁኝና ጠራሁኝ፣ ከዚያ ሁለት ጋዜጣ ገዛሁኝ፣ ወደ መኖርያዬ ተመልሼ ሳነብ ግን የልበወለድ አፍቃሪ ስለነበርኩኝ በአዲስ አድማስ ተማረኩኝ፣ ከዚያ ትውውቅ ወዲህ የአዲስ አድማሰ አንባቢ ብቻ ሳይሆን ሰብሳቢ ሆንኩኝ። እዚያ ከተማ ስሄድ የሳምንቱን ብቻ ሳይሆን ያለፈውን ጭምር እየገዛሁ አስቀምጣለሁኝ።
በእርግጥ አሁን በከተማዋ ውስጥ ራስ የሚያዞር ጸሐይ እንጂ ጋዜጣ የሚያዞር የለም። ያም ሆኖ ዕድሉ ሲገኝ በአካል ካልተገኘ በኦንላይን አነባለሁኝ። የምወደው ጥበብ የሚሰኘውን አምድ ነው፡፡ ጋዜጣውን በሙሉ ባነብም መጀመርያ ግን የኤፍሬም እንዳለን ሥራና አጭር ልበወለድ ነው የማነበው፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ አንብቤ የማስታውሰው አጭር ልበወለድ “ጭልፊቱ” የተሰኘው ትርጉም ልበወለድ ነው፣ አቤት አፍቃሪው ፌዴሪጎ እንዴት አሳዝኖኝ ነበር፣ እንዴት አስደስቶኝ ነበር፤ ለስንት ሰውስ ተረኩት። ይህን አጭር ልበወለድ የያዘው ህዳር 3 ቀን 2009 ዓ.ም ዕትም አሁንም ድረስ አለኝ። እና አዲስ አድማስ አንጀት የምታርስ፣ እኔን ከመሻቴ የምታደርስ ስለመሰለኝ ከተዋወቅኋት ቀን ጀምሮ እስካሁን ድረስ አነባታለሁ፡፡ እውንም በአዲስ አድማስ ተምሬአለሁኝ፣ተዝናንቻለሁኝ፤ ተሻሽያለሁ፡፡ አሁን ደግሞ እንደ ድሮ ጅማ እየተገኘች እንደልብ አነባት ዘንድ እናፍቃለሁኝ።
(ከድር ነብሶ)

Addis Admass

17 Jan, 20:14


ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ የተዋወቅሁት አርሲ ነጌሌ ከተማ ሞኪያ የተባለ የመጻሕፍት መደብር ውስጥ ከብዙ መጽሔቶች ጋር ተጀቡና በተመለከትኩበት ወቅት ነው። መኮንን በተባለ በመጻሕፍት ቤቱ ባለቤት በኩል አዲስ አድማስ ጋዜጣ ለከተማችን አንባብያን የመጣችው ለአጭር ጊዜ ቢኾንም፣ በኤፍሬም እንዳለ ወጎች፣ በአሰፋ ጫቦ የትዝታ ፈለጎች፣ በነቢይ መኮንን ተረቶች የታጠኑ ርዕሰ አንቀጾች፣ በዓለማየሁ አንበሴ ወቅታዊ ዜናዎች፣ በእነ ሌሊሣ ግርማ መጣጥፎች ፍቅር ለመውደቅ ግን ከበቂ በላይ ጊዜ ነበር። ይህች የቅምሻ ተጽዕኖ፣ ጎንደር ዩኒቨርስቲ በገባሁ ወቅት የማራኪ ካምፓስ ቤተ-መጻሕፍት ውስጥ ባለው የጋዜጣ ኮርነር ጋር የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ቀበኛ እንድኾን አድርጎኛል።
እንኳን ለ25ኛ ዓመት አደረሳችሁ/ አደረሰን
(ቢንያም አቡራ)

Addis Admass

17 Jan, 20:10


አዲስ አድማስን ማንበብ የጀመርኩት ገና ታትማ መውጣት ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ ነው። በወቅቱ Yellow journalism የተስፋፋበትና ጋዜጣ ከbroadsheet ወደ tabloid የተሸጋገረበት ጊዜ ነበር። ይልቁንም tabliod ጋዜጦች በነባር ጋዜጠኞች አሉታዊ አስተሳሰብ ሥር ነበሩ። አዲስ አድማስ ግን በ100 ከሚቆጠሩ ታብሎይድ ጋዜጦች ነጥራ ወጥታለች። ሆኖም የስፖንሰር አለመኖርና የወረቀት ዋጋ መጨመር እንዲሁም ወደፊት በሚመጣው የግብር ጫና ትቀጥል ይሆን? የሚል ስጋት አለኝ። እስካሁን ያቆዩዋትን በግሌ አመሰግናለሁ።
(ተሾመ ብርሃኑ ከድር)

Addis Admass

17 Jan, 20:07


አዲስ አድማስን ከ13 አመታት በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ደብረ ማርቆስ ተማሪ በነበርኩበት ወቅት ነው የተዋወቋት። ጋዜጣዋ ቅዳሜ ከሰዓት አንዳንዴ ደግሞ እሁድ ጠዋት ትደርስ ነበር፡፡ በወቅቱ እሸት አማተር የጋዜጠኞች ክበብ አባላት በተራ እየገዛን በፍቅር የምናነባት ተወዳጅ ጋዜጣ ነበረች። ለጋዜጣው አዘጋጆች ፣ አምደኞችና በትጋት ለምታነቡ የአዲስ አድማስ ወዳጆች በሙሉ እንኳን 25ኛ አመት የምስረታ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን!
ጌትነት ተመስገን(ጌች ሐበሻ)

Addis Admass

17 Jan, 19:59


"የጥምቀት በዓልን ለመታደም የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል ተዘጋጅተናል"

በጎንደር ከተማ አስተዳደር ከተለያዩ ማኅበራትና አደረጃጀቶች የተውጣጡ ወጣቶች ከከተማዋ ከፍተኛ የሥራ ኅላፊዎች ጋር የተወያዩ ሲሆን፤ ወጣቶቹ በከተማዋ እየተከናወኑ ያሉ የልማት ሥራዎች ተስፋ ሰጭ መሆናቸውን በውይይት መድረኩ ላይ ተናግረዋል፡፡

በዘንድሮው የጥምቀት በዓል ወደ ጎንደር ከተማ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበልና ተገቢውን መስተንግዶ እንዲያገኙ በባለቤትነት ስሜት እንሠራለንም ብለዋል። በውይይቱ ላይ የተገኙት የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው በበኩላቸው፤ ወጣቶች ለከተማዋ ሰላም በትኩረት መሥራት ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡ በከተማዋ የሚፈጸሙ ሕገ ወጥ ተግባራትን በመከላከል የከተማዋን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ መሥራት እንደሚገባቸውም ተናግረዋል፡፡

የዘንድሮ የጥምቀት በዓል ያለ ምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወን ሰፊ ሥራ ተሠርቷል ያሉት ምክትል ከንቲባው፤ የከተማው ወጣቶች እንግዶችን በመቀበልና በማስተናገድ፣ የአካባቢን ሰላም በመጠበቅ፣ ሊፈጸሙ የሚችሉ የስርቆት ወንጀልና ሌሎች ወንጀሎችን የመከላከል ሥራዎችን በማከናወን ግንባር ቀደም ሆነው ሊሠሩ እንደሚገባ ማሳሰባቸውን የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ዘግቧል፡፡

Addis Admass

17 Jan, 19:45


ፕሮፌሰር በላይ ወልዱ በበኩላቸው፤ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ በሙያቸው ለሃገራቸው የሰሯቸውን ስራዎች በመጥቀስ፣ አድናቆትና አክብሮታቸውን የገለጹ ሲሆን፤ “እንኳን ለ85ኛ ዓመትህ አደረሰህ! አሁንም ረጅም እድሜ እመኝልሃለሁ” ሲሉም መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ሌላው በፕሮግራሙ ላይ የታደመው ደራሲ ዘነበ ወላ፣ ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ለሃገር ያበረከቱትን አስተዋፅኦና የንባብ ባህል በማድነቅ፣ ወጣቶች ከእርሳቸው የንባብ ባህል ብዙ ሊማሩ እንደሚገባ ተናግሯል:: ጋዜጠኛ እዝራ እጅጉ ደግሞ የፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላን የሕይወት ታሪክ ለታዳሚው አንብቧል::

ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ለታዳሚው ባሰሙት ንግግር፤ "በጓደኞቼ አማካይነት ከብዙ ንግግር በኋላ ወደ እዚህ እንድመጣ የተነገረኝ በመፅሐፍህ ላይ ውይይት አለ ተብዬ ነው:: እዚህ ስደርስ ግን የሆነው ሌላ ነው:: በዛሬው ዕለት የ85ኛ ዓመት ልደቴን በማስመልከት፣ ይህን አይነት ፕሮግራም ስለተዘጋጀልኝ ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ" ብለዋል፡፡ በመጨረሻም ፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ከታዳሚው ጋር የመፅሐፍ ፊርማና የፎቶግራፍ ፕሮግራም አካሂደዋል::

የፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ የ85ኛ ዓመት የልደት ቀንን አስመልክቶ የተዘጋጀው የአክብሮትና የምስጋና መርሃግብር እንዲሰምር ከፍተኛውን አስተዋፅዖ ያደረገችው ወ/ሮ ሐና ይገዙን (ቡክ ኮርነር) ከልብ እናመሰግናለን:: በተመሳሳይ ሲቲ ሐሰን (ዋሊያ መፅሐፍት)፣ ሠዓሊ ወንደሰን ከበደ፣ ሠዓሊ መስፍን መብራቱ፣ ደራሲ በሁሉም አለበል እና የማስታወቂያ ባለሙያው ቢንያም ዮሐንስንም እንዲሁ ከልብ እናመሰግናለን::

Addis Admass

17 Jan, 19:44


ፕሮፌሰር ኤመረተስ ሽብሩ ተድላ በ85ኛ ዓመት
ልደታቸው ክብርና ምስጋና ተቸራቸው


የፕሮፌሰር ኤመረተስ ሽብሩ ተድላ 85ኛ ዓመት የልደት ቀናቸውን ምክንያት በማድረግ የአክብሮትና የምስጋና ፕሮግራም ትላንት ሐሙስ ጥር 8 ቀን 2017 ዓ.ም በዋሊያ መፅሐፍት አዳራሽ በድምቀት ተካሄደ::

የእኚህን ታላቅ ኢትዮጵያዊ ምሁር 85ኛ ዓመት የልደት ቀን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው የአክብሮትና የምስጋና ፕሮግራም ላይ የፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ጓደኞች የሆኑት ፕሮፌሰር ዘሪሁን ወልዱና ፕሮፌሰር በላይ ስማኒ፣ “እንኳን ለ85ኛ ዓመት የልደት ቀንህ አደረሰህ” ብለው የክብር ካባ አልብሰዋቸዋል::

ሠዓሊ ወንደሰን ከበደ በበኩሉ፣ ለፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ ያለውን ከፍተኛ ክብርና ምስጋና ለመግለፅ ያዘጋጀውን፣ የኢትዮጵያን የ7500 ዓመት ታሪክ የሚተርክ በነሐስ የተቀረጸና "ማሆጋኒ " በተሰኘ ልዩ እንጨት የሰራውን የጥበብ ስራ አበርክቶላቸዋል፡፡

በተጨማሪም፣ ሠዓሊ መስፍን መብራቱ፣ በእንጨትና በወርቅ ቅብ መደብ የሰራው ልዩ ሥጦታ ለእኚሁ ምሁር ተበርክቶላቸዋል፡፡

በዚህ ፕሮግራም ላይ ንግግር ያደረጉት የፕሮፌሰር ሽብሩ ተድላ የቀድሞ ተማሪና ጓደኛ ፕሮፌሰር ዘሪሁን ወልዱ፤ "ጋሽ ሽብሩ እድሜውን ሙሉ በማስተማር በመመራመር ለሐገሩ ብዙ የሰራ፣ አሁንም እየሰራ ያለ ታላቅ ኢትዮጵያዊ ነው:: ለሐገር ወዳዱ ኢትዮጵያዊ ምሁር የ85ኛ ዓመት የልደት ቀኑን በማስመልከት ይህንን ፕሮግራም ያዘጋጃችሁትን በሙሉ ከልብ አመሰግናለሁ:: ጋሽ ሽብሩ እንኳን ለ85ኛ ዓመትህ አደረሰህ!" ብለዋል፡፡

Addis Admass

17 Jan, 19:36


በኢትዮጵያ ከፍተኛ መዋእለ ንዋይ በማፍሰስ የገበያ ተደራሽነቱን እያሰፋ የሚገኘው ኩባንያው፤ የሰራተኛ ቅጥርንም ገበያው በሚፈልገው ልክ እያሳደገ መሆኑ ተጠቁሟል።

መረጃዎች እንደሚጠቁሙት፤ ባለፉት ሁለትና ሦስት አመታት በአገሪቱ የስራ አጥነት ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እየጨመረ ሲሆን፤ ይሄንን ችግር ለመቅረፍም የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን የማበረታታት አስፈላጊነት ሲገለፅ ቆይቷል።

ይሁንና የኮካ ኮላ መጠጦች አፍሪካ (ሲሲቢኤ)፣ በኢትዮጵያ የፈጠረው ከፍተኛ የስራ እድልና የቅጥር አድማስ፣ የ2025 ከፍተኛውን የዕውቅና ማዕረግ ለመያዝ እንዳስቻለው ለማወቅ ተችሏል።

የኮካ ኮላ መጠጦች አፍሪካ፣ የኢትዮጵያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዳሪል ዊልሰን ሲናገሩ፤ "ሽልማቱ ኩባንያው ከፍተኛ አቅምና አፈጻጸም ያላቸውን ሰራተኞች ለመሳብና ለማቆየት እንዲሁም፣ በሰው ሐብት አስተዳደር እድገት ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ያለውን አቋም ያንፀባርቃል" ብለዋል።

የኮካ ኮላ መጠጦች አፍሪካ (ሲሲቢኤ)፤ በአፍሪካ ከ18 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ሲሆን፤ በአለማቀፍ ደረጃ ከ720 ሺህ በላይ ደንበኞች እንዳሉት "ቶፕ ኢምፕሎዪ ኢንስቲትዩት" ጠቁሟል። ኩባንያው በ15 ሀገራት ውስጥ የሚሰራ ሲሆን፤ ስድስት ቁልፍ ገበያዎቹ ደቡብ አፍሪካ፣ ኬንያ፣ ኢትዮጵያ፣ ኡጋንዳ፣ ሞዛምቢክና ናሚቢያ ናቸው። በተጨማሪም በታንዛኒያ፣ ቦትስዋና፣ ጋና፣ ዛምቢያ፣ ኮሞሮስ፣ ኢስዋቲኒ፣ ሌሶቶና ማላዊ ከፍተኛ ገበያ እንዳለው ተገልጿል።

በተቋሙ መስፈርት መሰረት፣ ኩባንያዎች የከፍተኛ ቀጣሪነት (Top Employer) የዕውቅና ሽልማት የሚያገኙት የሥራ ከባቢያቸው፣የሠራተኞችን አቅምና ችሎታ ለማጎልበት የሚያደርጉት ጥረቶች፣ አካታችነት፣ እንዲሁም በአጠቃላይ የሰው ሃብታቸውን ለማበልጸግ ያላቸው ቁርጠኝነት ከተገመገመ በኋላ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

Addis Admass

17 Jan, 19:36


የኮካ ኮላ መጠጦች አፍሪካ በኢትዮጵያ "ከፍተኛው ቀጣሪ" ተባለ

የኮካ ኮላ መጠጦች አፍሪካ (ሲሲቢኤ)፤ በኢትዮጵያ የ2025 ከፍተኛ ቀጣሪ ኩባንያ መሆኑን "ቶፕ ኢምፕሎዪ ኢንስቲትዩት" የተሰኘ ተቋም አስታወቀ። ተቋሙ ባካሄደው ጥናት መሰረት፤ ኩባንያው በኢትዮጵያ ውስጥ የ2025 የከፍተኛ ቀጣሪ ደረጃ እውቅና ካገኙ ስድስት ኩባንያዎች ውስጥ አንዱ ሆኗል፡፡

Addis Admass

16 Jan, 20:48


የጥምቀት በዓል ሃይማኖታዊ እሴቱን እና የቱሪስት መስህብነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ተባብረን በጋራ እንስራ :-ከንቲባ አዳነች አቤቤ


የጥምቀት በዓል ሃይማኖታዊ እሴቱን እና የቱሪስት መስህብነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ተባብረን በጋራ እንስራ ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ የትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት ማምሻውን የጥምቀት በዓልን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አባቶች ጋር መወያየታቸውን ገልጸዋል፡፡

የጥምቀት በዓል የተለመደውን ሃይማኖታዊ እሴቱን ጠብቆ በደመቀ ሁኔታ እንዲከበር ለማድረግ ከሃይማኖቱ አባቶች ጋር ተወያይተናል ያሉት ከንቲባ አዳነች ሁላችንም በዓሉ ሃይማኖታዊ እሴቱን እና የቱሪስት መስህብነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ተባብረን በጋራ እንስራ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Addis Admass

15 Jan, 20:22


ውድ ከሆነ ጊዜያቸው ላይ ቀናንሰው ለወራት የአዲስ አድማስ አንባብያንን በተባ ብዕራቸው አጥግበዋል፤አንዳንዶቹም እስካሁን ቀጥለውበታል፡፡ (ሐሙስ ሐሙስ ከሌሊቱ 8 እና 9 ሰዓት ላይ ጽሑፋቸውን አጠናቀው የሚልኩልን ነበሩ) ባለፈው ሳምንት ለ25ኛ ዓመት ልዩ ዕትምም ጥሪያችንን ሰምተው የጋዜጣዋ የቀድሞ ጸሓፍት በብዛት ተሳትፈዋል፡፡

እነዚህ የአዲስ አድማስ ወዳጆችና አንጋፋ ጸሓፍት ራሳቸው ብቻ በመጻፍ ሳይወሰኑ፣ ሌሎች በሳል ጸሓፍትም እንዲጽፉ ጋብዘዋል፤ ጠቁመዋል፤ አሁንም ያንኑ ከማድረግ አልቦዘኑም፡፡

ከሁሉም የሚገርመው ደግሞ አንጋፋ ጸሓፍቱ በአብዛኛው የሚተዋወቁና ወዳጆችም በመሆናቸው “ለአዲስ አድማስ ጻፍ እንጂ” እየተባባሉ አንዳቸው ሌላኛቸውን ማትጋታቸው ነው፡፡ ይህን ሁሉ የሚያደርጉት ደግሞ ለጋዜጣው ባላቸው ጥልቅ ፍቅርና የመቆርቆር ስሜት ነው፡፡ ስለዚህም በአንባቢዎቻችን ስም ከልብ ልናመሰግናቸው እንወዳለን፡፡ "ብዕራችሁ ይለምልም!" ምርቃታችን ነው፡፡

በቅርቡ አዲስ አድማስን ተቀላቅለው በትጋት እየጻፉና ሃሳባቸውን እያቀበሉ የሚገኙ ጸሃፍትም እንዲሁ ምስጋና ይገባቸዋል፤ ለጋዜጣው ዕውቀትና ውበት ሆነዋልና፡፡

ላለፉት በርካታ ዓመታት፣ በጋዜጣዋ ላይ ምርትና አገልግሎታቸውን በማስተዋወቅ በአጋርነት የዘለቁ የግል የንግድ ድርጅቶችና የመንግሥት ተቋማትም በተመሳሳይ ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል፡፡ ያለ እነርሱ የፋይናንስ ግብአት የዛሬዋ ቀን ላይ መድረስ አይታሰብምና፡፡

እንግዲህ አንጋፋዋ አዲስ አድማስ በየሳምንቱ ሳትቋረጥ እየታተመች ለ25ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓሏ የደረሰችው በእነዚህ ሁሉ ወገኖች ድጋፍና አስተዋጽኦ ነውና ለሁሉም ክብረት ይስጥልን ትላለች፡፡ በሌላ የምስጋና ቃላት እንመለሳለን፡፡

አዲስ አድማስ - የእርስዎና የቤተሰብዎ

Addis Admass

15 Jan, 20:21


ለ25ኛ ዓመታችን የደረስነው በእናንተ ፍቅርና ድጋፍ ነው!


በዚህ የአዲስ አድማስ የ25ኛ ዓመት የምሥረታ ክብረ በዓል ላይ ሆነን ባለፉት ዓመታት ያሳለፍናቸውን ውጣ ውረዶች፤ ወይም አሁን ያለንበትን አጣብቂኝ ከመዘክዘክ ይልቅ በዓሉን በምስጋና ማሳለፍ ይሻላል ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ጉዟችን ሞልተው የተትረፈረፉ በረከቶች ተችሮናልና፡፡ በዚህም መሠረት የምስጋና ቃላት እነሆ - ምስጋና ለሚገባቸው፡፡

ስለዚህም፣ከሁሉ በፊት ውድ አንባቢዎቻችንን ከልብ ልናመሰግን እንወዳለን፡፡ ለዓመታት ወደውና መርጠው ስላነበቡን፤ከፊደል ግድፈቶቻችን ጀምሮ ስህተቶቻችንን ስለጠቆሙንና ስላረሙን፣ እንዲሁም ሳያሰልሱ ሃሳብ አስተያየታቸውን ስላቀበሉን ምስጋናችን ወደር የለሽ ነው።

በመለጠቅ የምናመሰግነው የአዲስ አድማስን የረዥም ዘመን “ወዳጅ ጸሓፍትን” ነው፡፡ ለምን ቢባል ትልቅ ባለውለታዎች ናቸውና፡፡ እስቲ ለአብነት ያህል ጥቂቱንና የቅርብ ጊዜውን እናንሳ፡፡ ባለፈው ዓመት፣ ዝግጅት ክፍላችን የአዲስ አድማስ 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል መቃረብን ምክንያት በማድረግ፣ ከጋዜጣዋ ላይ ለጠፉ የረዥም ጊዜ ወዳጆችና ጸሓፍት አንድ ጥያቄ አቅርቦ ነበር - “አዲስ አድማስን ተባብረን ወደ ወርቃማ ዘመኗ” እንመልሳት የሚል፡፡

የአንጋፋ ጸሓፍቱ ምላሽ ልብ የሚያሞቅ፣ በደስታ የሚሞላና በተስፋ የሚያጥለቀልቅ ነበር፡፡ “ጋዜጣዋ እኮ የሁላችንም ናት፤ሳንጠየቅ ነበር ይህን ማድረግ የነበረብን”፣ “ያሳደገችንን ጋዜጣ መደገፍ ግዴታችን ነው”፤ “አንድ የቀረችንን ጋዜጣ በጋራ መታደግ አለብን” ወዘተ--የመሳሰሉ አስደሳችና ብሩህ ተስፋ የሚፈነጥቅ ምላሽ ነበር የሰጡን፤ቃላቸውንም በተግባር ፈጽመውታል፡፡ የአዲስ አድማስ ታማኝ ወዳጅነታቸውንም አስመስክረዋል፡፡

Addis Admass

15 Jan, 11:27


የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን ታሪካዊነት ይበልጥ የሚያጎላ ነው - ከንቲባ አዳነች አቤቤ
*
የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ የከተማዋን ታሪካዊነት ይበልጥ የሚያጎላ እና የቱሪስት መዳረሻነቷን የሚያሳድግ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ፡፡

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፤ ዛሬ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር፣ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው እና ከምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ጋር በመሆን የጎንደር የኮሪደር ልማት እና የፋሲለደስ ግንብ እድሳት የደረሰበትን ደረጃ ጎብኝተናል ብለዋል።

የጎንደር ከተማ የኮሪደር ልማት ስራ እና የፋሲለደስ እድሳት እጅግ በጣም ውብ፣ የከተማዋን ታሪካዊነት ይበልጥ በሚያጎላ እና የቱሪስት መዳረሻነቷን በሚያሳድግ ሁኔታ በመሰራት ላይ ነው ሲሉም ገልፀዋል።

በዚህ የለውጥ ዘመን የኢትዮጵያ ከተሞች የተሰጣቸው ትኩረት እጅግ ትልቅ ነው ያሉት ከንቲባዋ፤ በተለይም ለነዋሪዎቻቸው ምቹ እና ውብ እንዲሁም ለቱሪስት መስህብ መሆናቸውን እጅግ የሚጨምር ስራ በመሰራት ላይ ይገኛል ብለዋል።

Addis Admass

15 Jan, 09:41


በጎንደር ከተማ እየተካሄዱ ያሉት የፋሲለደስ እድሳት እና የኮሪደር ልማት ሥራዎች እድገት እጅግ አበረታች ነው። በሥራው ለተሳተፉ ሁሉ በተለይም በክብር ለተሞሉት እንግዳ ተቀባይ የጎንደር ነዋሪዎች በሙሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናዬን ለመግለጽ እወዳለሁ።

Addis Admass

13 Jan, 20:09


ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ከዴንማርክ ልዕልት ጋር ተወያዩ
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከዴንማርክ ልዕልት ቤኔዲክቴ አስትሪድ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸውም በሕጻናት ድጋፍና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም ተደራሽ ለማድረግ በጋራ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

Addis Admass

12 Jan, 09:33


Channel photo updated

Addis Admass

12 Jan, 07:37


የበርካታ ሰዎች ቤት ወደ አመድነት ተቀይሯል።

ሰደድ እሳቱ ያደረሰው ውድመት 135 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ የተገመተ ሲሆን ከዚህም ከፍ እንደሚል ይጠበቃል።

Addis Admass

12 Jan, 06:35


በሎስ አንጀለስ በተከሰተው ሰደድ እሳት ምክንያት ከ137 ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል። እስካሁን ቢያንስ 10 ሰዎች ሲሞቱ፣ ያደረሰው ውድመት 135 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ የተገመተ ሲሆን፣ ከዚህም ከፍ እንደሚል ይጠበቃል።
እሳቱን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት ቢቀጥልም ዝነኛ ወደሆነው ሆሊዉድ እየተቃረበ ነው። በቀጣይ ቀናት ምን ሊከሰት እንደሚችል በእርግጠኛነት መተንበይ ባይቻልም ነዋሪዎች ለቀው እንዲወጡ ወይም ለመውጣት እንዲዘጋጁ ተነግሯቸዋል።

Addis Admass

11 Jan, 21:24


ግብር ከፋዩ በእጁ ያለው ማንዋል ደረሰኝ ከየካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት ላይ ስለማይው አዲሱን ደረሰኝ ከወዲሁ እንዲያሳትም ጥሪ ቀረበ ።

በአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የልደታ ክፍለ ከተማ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ስራ አስኪያጅ ወይዘሮ የኃላወርቅ ለማ ከዝግጅት ክፍላችን ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለፁት " አሁን አገልግሎት እየሰጠ ያለው ማንዋል ደረሰኝ ከየካቲት 02 / 2017 ዓ.ም ጀምሮ ጥቅም ላይ ስለማይውል ግብር ከፋዩ ይህን ተገንዝቦ ከወዲሁ አሳውቆ ወደ ህትመት እንዲገባ አሳስበዋል ።
ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቱ ከደረሰኝ ህትመት ጋር ተያይዞ እስካሁን የሰራቸው ስራዎች በተመለከተ ሀላፊዋ እንደገለፁት በአካል ሲመጡ ለግንዛቤ የተዘጋጁ ብሮሸሮች፣ በራሪ ወረቀት በመስጠት በቴሌ አጭር መልዕክት በመላክ ፣ በቅርንጫፉ ማህበራዊ የቴሌግራም ቻናል በመጠቀም ጭምር እንዲያውቁ መደረጉን ተናግረዋል
ከገቢ አሰባሰብ አንፃርበበጀት አመቱ በስድስት ወራት 1693,28ቢሊየን ብር ለመሠብሰብ ታቀዶ፣ 1701.72 ቢሊየን ብር የተሰበሰበ ሲሆን የዕቅዱን 100.5 ፐርሰንት ማሳካት መቻሉን ጠቁመዋል።
ግብርከፋዮች ጊዜ አለን በሚል መዘናጋት ደረሰኝ ሳያሳትሙ ለአላስፈላጊ እንግልትና ቅጣት እንዳይዳረጉ ከወዲሁ አሳውቀው ደረሰኝ እንዲያሳትሙ ሀላፊዋ መልዕክታቸውን አስተላልፈውል ።

Addis Admass

11 Jan, 21:22


የተወዳጁ አርቲስት ማህሙድ አህመድ የመጨረሻ መድረክ “ማህሙድ ኮንሰርት” በሺዎች የሚቆጠሩ አድናቂዎቹ በተገኙበት በሚሊኒየም አዳራሽ መቅረብ ጀምሯል።
የትዝታው ንጉስ ማህሙድ አህመድ የ60 ዓመት የመድረክ ቆይታ ሽኝት በድምቀት እየተካሄደ ነው፡፡
ከሽኝቱ በተጨማሪ ዛሬ 83ኛ ዓመት የልደት በዓሉም ተከብሯል።

Addis Admass

11 Jan, 20:57


በሎስ አንጀለስ የተከሰተውን እሳት ለመቆጣጠር እስረኞች እንዲሰማሩ የካሊፎርኒያ ግዛት ፈቃድ ሰጥታለች

በማረሚያ ቤቶች ውስጥ የሚገኙት እስረኞች መጠነኛ ስልጠና ወስዷው እሳቱን ለመቆጣጠር እያገዙ ነው ተብሏል

Addis Admass

11 Jan, 20:25


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የሶማሊያ ፕሬዚዳንት ተቀበሉ


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን የሶማሊያ ፌዴራል ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ ተቀብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት "የሶማሊያ ፌዴራል ሪፐብሊክ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐሙድ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ እንኳን ወደ ኢትዮጵያ መጡ እላለሁ።" ብለዋል።

Addis Admass

11 Jan, 11:50


ጊዜው እንዴት ይሮጣል ጃል
‹‹አዲስ አድማስ ይታየኛል››


በ‹‹አዲስ አድማስ›› ልደት ለመገኘት፤ በኮከቡ አሰፋ እየተመሩ ከተጓዙ ‹‹ሰብአ ሰገሎች›› መካከል፤ ነቢይ
መኮንን፣ ሰለሞን ገ/እግዚአብሔር፣ ብርሃኑ ነጋሽ እና የዚህ ጽሁፍ አቅራቢ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ ማርቆስ ረታን
ጨምሮ፤ ነቢይ፣ ሰለሞን፣ ብርሃኑ ኦርማ ጋራዥ አካባቢ በነበረው የ‹‹አዲስ አድማስ›› ቢሮ፤ Backlog
እየሰሩ ጥቂት ወራት እንደ ቆዩ ነበር እኔ የተቀላቀልኳቸው፡፡ ወዲያው ቢሮ ቀየርን፡፡ ከኦርማ ጋራዥ ወደ
‹‹ሴንትራል ሸዋ›› አካባቢ ተዛወርን፡፡ የ‹‹አዲስ አድማስ›› የመጀመሪያ ዕትም ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም
ለገበያ ቀረበ፡፡ የ25 ዓመታቱም ጉዞ ተጀመረ፡፡

Addis Admass

11 Jan, 11:29


በአዲስ አበባ ከ112 ሺህ በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እየወሰዱ ነው


በአዲስ አበባ ባለፉት ስድስት ወራት ከ112 ሺህ በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እየተከታተሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ሐሳብ አመንጪነት ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ 5 ሚሊዮን ዜጎችን የዲጅታል ክህሎት እንዲያገኙ የሚያስችል የኮደርስ ኢኒሼቲቭ እየተተገበረ ይገኛል።

አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚሰጠው ስልጠናም የዳታ ሳይንስ፣ ኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ ሞባይል አንድሮይድና የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፎችን ያካትታል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ ሰለሞን አማረ እንዳሉት የኮደርስ ስልጠና በአዲስ አበባ የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትን እውን ለማድረግ ትልቅ አቅም ይፈጥራል።

በተለይም የዲጂታል እውቀትና ክህሎታቸው ያደገ ሙያተኞችን ለማፍራት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በ2017 በጀት ዓመት እስክ ታህሳስ 30 ድረስ ከ112 ሺህ በላይ ወጣቶች የኮደርስ ስልጠና እየተከታተሉ እንደሚገኙም ገልጸዋል።

ከእነዚህ መካከልም እስከ 30 ሺህ የሚሆኑ ወጣቶች ስልጠናውን በሚገባ በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት መውሰዳቸውን ተናግረዋል።


ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ጋር በመተባበር ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ሙያተኞች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መሰጠት መጀመሩን መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

Addis Admass

11 Jan, 05:47


ሎስአንጀለስን ሞቅናት!
(በእውቀቱ ስዩም)
ትናንትና ሎስአንጀለስ በእሳት ስትነድ፥ እኔ በአጋጣሚ ጓደኞቼን ለመሰናበት እዚያው ከተማ ውስጥ ነበርሁ፤ ሆሊውድ አካባቢ በእግሬ እየተንሸራሸርሁ ድንገት ቀና ብየ ሳይ፥ ከተማው እንደ ደመራ ይንቦገቦጋል፤ መጀመርያ ላይ ፥የዮዲት ጉዲትን ፊልም እየሰሩ ነበር የመሰለኝ፤ ብዙ ሳይቆይ የሳት አደጋ መኪና እየተብለጨለጨ ባጠገቤ አለፈ፤
ነገሩ “ሲርየስ” መሆኑን ያወቅሁት፥ የሆሊውድ አክተሮች ልጆቻቸውን እንኮኮ አዝለው፥ የቤት እቃቸውን ባንሶላ ጠቅልለው፥ ሲራወጡ ስመለከት ነው ፤ ደንብ አስከባሪ የሚያባርራቸውን የመገናኛ ቦንዳ ሻጮችን አስታወሱኝ፤ ቻክኖሪስ ባንድ የእሳት አደጋ ሰራተኛ ታዝሎ፥ ሳል እያጣደፈው ከቤቱ ሲወጣ አይቼ “እድሜ አተላ “ብየ ተከዝኩ::
እያወካ እየተጋፋ ከሚሸሸው ሰው መሀል ተቀላቅየ መሮጥ ጀመርሁ፤
ቀጣዩ ፌርማታ ላይ ትንፋሽ ለመሰብሰብ ቁጭ ባልሁበት፥ የሆነ ፖሊስ መጣና፤
“Are you ok?” አለኝ፤
“ እድሜ ልኬን ለፍቼ፥ እቁብ ጥየ ፥ ያፈራሁት ቤቴና ንብረቴ በእሳት ጋየ” ብየ መለስኩለት፤
“ስራህ ምንድነው ?”
መቸም በዚህ ሰአት ላይ ሊያጣራ አይችልም ብየ በማሰብ፥
“ ቀን የጣለኝ የሆሊውድ አክተር ነኝ “ አልሁት፤
“ምን ፊልም ላይ ሰርተሀል?”
”በማርቲን ሉተር ኪንግ የህይወት ታሪክ ዙርያ፥ በሚያጠነጥን ፊልም ውስጥ ከበድ ያለ ሚና ነበረኝ ” አልሁት፤
ፖሊሱ አልተፋታኝም፤
“ምን ሆነህ ነው የተወንከው?”
“ ማርቲን ሉተርኪንግ ፥ ሁለት መቶ ሺህ ህዝብ ሰብስቦ ንግግር የሚያደርግበት ትእይንት ትዝ ይለሀል?” አልኩት፤
“አዎ”
“ ከህዝቡ መሀል አንዱን ሆኜ ተውኛለሁ፤ ፊልሙ ጀምሮ አንድ ሰአት ከሶሰት ደቂቃ ከአምሳ ሁለት ሰከንድ ላይ ራሱን እሚነቀንቀው ሰውየ እኔ ነኝ “
ፖሊሱ ጥሩ ሰው ነው፤ ወስዶ ከተፈናቃዮች ጋራ ቀላቀለኝ፤ የከተማው ከንቲባ ዘለግ ያለ ንግግር አደረጉ ፤” የተወደዳችሁ ተፈናቃዮች ሆይ ! የከተማው አስተዳደር ቤታችሁን መልሶ እስኪገነባ ድረስ ባለ አምስት ኮከብ ሆቴል ውስጥ ልናቆያችሁ እንገደዳለን ”ብለው ንግግራቸውን አሳረጉ

በመጨረሻ” የአደጋና ስጋት መስርያ ቤት” ሊቀመንበር ወደኔ ቀርቦ፥
“ የደረሰብህን ኪሳራ እስክናጣራ ፥ይቺን ነገር ላንዳንድ ነገር ትሁንህ “ አለና አምሳ ሺህ ዶላር የያዘች ትንሽ ብጫ ፌስታል አስጨበጠኝ፤
ብዙም ሳልቆይ፥ፌስቡኬ ላይ የሚከተለውን ማሳሰቢያ ጣል አረግሁ፤
Bewketu Seyoum marked himself safe from poverty .

Addis Admass

11 Jan, 05:40


መጭውን ጠበቅሁት
(በእውቀቱ ስዩም)
'ከማዶ እሚመጣው፥ ዘመድ ነው እንግዳ
ከላይ የተለጋው፥ ኳስ ነው ወይስ ናዳ?'
ብየ መች ጠየቅሁኝ፤?
መጭውን ጠበቅሁት...
ድንጋይ ላይ ቁጭ ብየ፤ ጸሀይ እየሞቅሁኝ፥
መከራም አላጣም፥ ተድላም አልጎደለኝ
ደንታ ነው የሌለኝ።
ባካል በስሜትም፥ ታሞ ላገገመ
ወድቆ ለተነሳ ፥ እየደጋገመ፤
ከገዛ ጉድጓዱ ፥አጽሙን ለሚለቅም
ሞትም ብርቅ አይደለም፥ ትንሳኤም አይደንቅም ::

Addis Admass

11 Jan, 05:33


የአቶ ቡልቻ ደመቅሳ የቀብር ስነ-ስርዓት የፊታችን እሁድ ይፈፀማል


የአንጋፋው ፖለቲከኛ እና የምጣኔ ሀብት ባለሙያ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የቀብር ስነ-ስርዓት በመጪው እሁድ ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም ይፈፀማል፡፡

በዕለቱ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ አድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ የእርሳቸውን ክብር በሚመጥን መልኩ የአስክሬን ሽኝት እንደሚደረግም ተገልጿል፡፡

ከሽኝቱ በኋላ የቀብር ስነ-ስርአቱ ቤተሰቦቻቸው፣ የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት እሁድ ከቀኑ 7 ሰዓት በጴጥሮስ ወጳውሎስ መካነ መቃብር እንደሚፈፀም ታውቋል፡፡

Addis Admass

11 Jan, 05:30


ውድድራችሁ ከራሳችሁ ግብ ጋር ይሁን

ራሳችሁን ከሌሎች ሰዎች ጋር ማወዳደርንና መፎካከርን ያቆማችሁ ቀን ውድድሩን ሁሉ የምታሸንፉት ያን ጊዜ እንደሆነ አትዘንጉ፡፡

ከሌላው ሰው አንጻር መኖርና በልጦ ለመገኘት መሯሯጥ ተሸንፎ መጀመር ማለት ነው፡፡

ከሰዎች ጋር ያላችሁ ፉክክር አሸንፋችሁ ከብቃታችሁ በታች ወርዳችሁ ልትገኙ ትችላላችሁ፡፡

ይህ እንዳይሆን፣ ከሕይወታችሁ ዓላማ አንጻር ግባችሁን ከፍ አድርጋችሁ አውጡና ውድድራችሁን ከእሱ አንጻር አድርጉት፡፡

Dreyob

Addis Admass

11 Jan, 05:19


አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቱሪስቶች ክልሉን ጎብኝተዋል

በበጀት ዓመቱ ባለፉት ስድስት ወራት አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ቱሪስቶች የአማራ ክልል መጎብኘታቸውን የክልሉ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ።
በዚህም ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ሁለት ነጥብ አራት ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን ቢሮው ጨምሮ ገልጿል፡፡
የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ አባይ መንግስቴ ለጋዜጣ ፕላስ እንዳስታወቁት፤ ባለፉት ስድስት ወራት አምስት ነጥብ ሁለት ሚሊዮን ቱሪስቶች የክልሉን የተለያዩ ቦታዎች ጉብኝተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገራት ጎብኚዎች አራት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ለማግኘት ታቅዶ እየተሰራ ነው ያሉት ምክትል ቢሮ ኃላፊው፤ በክልሉ የቱሪስት የቆይታ ጊዜ የሚያራዝሙና የታቀደውን እቅድ ለማሳካት የሚያስችሉ በርካታ ምቹ ሁኔታዎች አሉ ብለዋል፡፡
የልደት በዓልን ጨምሮ በቀጣይ በክልሉ በጥር ወር የሚከበሩ ሐይማኖታዊና ባህላዊ በዓላት የክልሉን የቱሪዝም እንቅስቃሴ ይበልጥ እንደሚያሳድግ አብራርተዋል፡፡
(ኢፕድ)

Addis Admass

10 Jan, 21:51


Here's a highly reliable online part-time job platform that I would like to recommend to you: BTT.

BTT is one of the largest advertising networks globally and is currently recruiting online part-time employees in Ethiopia.

No academic qualifications or work experience are required, and you can easily start earning money with just a smartphone. By downloading the designated app and increasing the download rate of other companies, you can earn lucrative referral fees.

💸 Daily income up to 4,000 ETB
📱Simple operation, only 15-20 minutes per day
Free without any investment
📈 Provides exclusive training to help you

If you are interested in this opportunity
please click the BTT official channel to contact customer service:
https://t.me/+fKeyX9Wh95wxMWNl

Addis Admass

10 Jan, 20:06


የነዳጅ ምርቶችን "ሆን ብሎ" ከባዕድ ነገሮች ጋር በመቀላቀል ለግብይት ማቅረብ ከአምስት ዓመት እስከ ሰባት ዓመት በሚደርስ እስራትና ከ350 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ አዋጁ ላይ ሰፍሯል። ሌላው ለቅጣት የሚያስከትለው ድርጊት፣ መንግሥት ከተመነው የመሸጫ ዋጋ በላይ የነዳጅ ምርቶችን መሸጥ ነው። ይህ ድርጊት ለመጀመሪያ ጊዜ ሲፈጸም ቅጣቱ ከ300 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር ሲሆን፤ ድርጊቱ በተደጋጋሚ ከተፈጸመ ከሦስት ዓመት እስከ አምስት ዓመት እስራትና ከ350 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር ድረስ ያስቀጣል።

የነዳጅ መቅጃ መሳሪያዎች የልኬት ሜትር ማስተካከያ ተደርጎበት በፕሎምፕ የታሰረውን መቁረጥ ወይም ልኬቱን ማዛባትም በተመሳሳይ ከ350 እስከ 500 ሺህ ብር እንደሚያስቀጣ አዋጁ ደንግጓል። በአዋጁ መሰረት፤ የነዳጅ ውጤቶች ከተፈቀደለት የማጓጓዣ መስመር ውጪ ማጓጓዝ፣ ከተፈቀደለት ማራገፊያ ስፍራ ውጪ ማራገፍ ወይም ወደ ጎረቤት አገር በኮንትሮባንድ ማጓጓዝ፣ ከአምስት ዓመት እስከ አስር ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እና ከ400 ሺህ እስከ 700 ሺህ ብር ያስቀጣል። ከሚመለከተው አካል በጽሑፍ ፈቃድ ሳያገኝ የነዳጅ ውጤቶችን የነዳጅ ማደያ በሌለባቸው አካባቢዎች መሸጥ እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እስራትና ከ300 እስከ 500 ሺህ ብር የሚያስቀጣ ጥፋት ነው።

የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣንን ወይም የሚመለከተውን አካል የቁጥጥር ሂደት መቃወምና ማሰናከል ከአምስት ዓመት በማይበልጥ እስራትና ከ200 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር ያስቀጣል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ተወካይ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ በሰጡት አስተያየት፤ "ቅጣቶቹ በጣም የተጋነኑ ሆነው ነው ያየኋቸው" ብለዋል። አክለውም፤ "አዋጁ ቅጣት ላይ ብቻ ያተኮረ፤ ቅጣትን ማዕከል ያደረገ ነው" ብለዋል።

ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳሕረላ አብዱላሂ፤ "ቅጣቱን በተመለከተ ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር ተነጋግረን ነው ያስቀመጥነው" ብለዋል። "ቅጣቱ ከፍተኛ አይደለም" ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ;፤ "ነዳጁ ተሽጦ የሚገኘውን ትርፍ መጠንና ሊያደርስ የሚችለውን ጉዳት ስናይ፣ እዚህ ላይ የተቀመጡት የገንዘብ ቅጣቶች በጣም ትንሽ ናቸው" ሲሉ መልሰዋል።

አዋጁ በሁለት ተቃውሞ፣ በአንድ ድምጸ ተዓቅቦ፣ በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል።

Addis Admass

10 Jan, 20:06


አዋጁ የነዳጅ ነጋዴዎች ላይ ከነበረው ቢሮክራሲ በላይ ሌላ ተጨማሪ ተጽዕኖ እንዳያሳርፍ ስጋት እንዳላቸው የገለጹ አንድ የምክር ቤቱ አባል፤ “በነጋዴዎች ላይ ብቻ ሳይሆን ሃላፊነታቸውን ባልተወጡ የመንግሥት አካላት ላይ ቅጣት ቢጣል፣ አጠቃላይ እንቅስቃሴውን የተሳለጠ ሊያደርገው ይችላል፤ የነዳጅ ቦቴዎችን ለመቆጣጠር ከጂፒኤስ በተጨማሪ ሌሎች አማራጮችም መታሰብ አለባቸው" ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ባለፈው ሰኔ ወር ለምክር ቤቱ ቀርቦ የነበረው ረቂቅ አዋጅ ላይ ከነዳጅ ግብይት ጋር በተያያዘ የሚጣሉ የቅጣት ውሳኔዎች ላይ ማሻሻያዎች ተደርገውበታል። በአዋጁ መሰረት የነዳጅ ውጤቶችን ከተፈቀደው ቦታ ውጪ ያከማቸ፣ ሊሸጥ ከሚገባው ሰው፣ ቦታና የግብይት ሥርዓት ውጪ ሲሸጥ የተገኘ ማንኛውም ሰው፣ ከሦስት ዓመት እስከ አምስት ዓመት በሚደርስ እስራትና ከ350 ሺህ እስከ 500 ሺህ ብር በሚደርስ መቀጮ ይቀጣል። ከዚህ በተጨማሪም፣ የተያዘው የነዳጅ ውጤት እንደሚወረስ አዋጁ ይደነግጋል፡፡

Addis Admass

10 Jan, 20:05


አዲሱ አዋጅ በነዳጅ ነጋዴዎች ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳርፍ ያሰጋል ተባለ

• ነዳጅ ከተተመነው ዋጋ በላይ መሸጥ ከ300 ሺህ- 500 ሺህ ብር ያስቀጣል


በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጸደቀው የነዳጅ ውጤቶችን ግብይት ስርዓት ለመደንገግ የወጣው አዲስ አዋጅ፤ በነዳጅ ነጋዴዎች ላይ ተጽዕኖ እንዳያሳርፍ ያሰጋል ተብሏል። አንዳንድ የምክር ቤት አባላት አዋጁ ግልጽ የውክልና አሰጣጥ ሂደትን "አልተከተለም" ሲሉ ነቅፈውታል።

ትላንት ሐሙስ ጥር 1 ቀን 2017 ዓ.ም. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣አንድ የምክር ቤቱ አባል፣ አዋጁ ግልጽ የውክልና አሰጣጥ ሂደትን "አልተከተለም" ሲሉ የተቹ ሲሆን፤ በየአንቀጹ "ወደፊት የአፈጻጸም መመሪያ ይዘጋጅለታል" መባሉንም እንደ አብነት አንስተዋል።

ይህም የአዋጁን የውክልና አሰጣጥ ሂደት ጥያቄ ውስጥ እንደሚያስገባ ያመለከቱት እኚሁ አባል፤ አዋጁ ከዚህ አንጻር ታይቶ ማሻሻያ እንዲደረግበት አሳስበዋል። ሌላኛዋ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው፤ ዓዋጁ በአሁኑ ወቅት የሚስተዋለውን የነዳጅ አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ እንደሚያስችል ገልጸው፣ "በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተለያዩ አላስፈላጊ ኬላዎች በመኖራቸውና አሽከርካሪዎች የተጋነነ ክፍያ እንዲከፍሉ በመደረጋቸው አቅርቦቱ ላይ የራሱን ተጽዕኖ እያሳረፈ ነው። የሚጠየቀው የኮቴ ክፍያ ፈታኝ ሆኗል። እዚህ ጉዳይ ላይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ መስራት አለበት።" ብለዋል።

Addis Admass

10 Jan, 19:55


ያለው ማማሩ….. ቅናቱ ገደለኝ

(ከአድማስ ትውስታ፤ 1992)

-አሰፋ ጫቦ-
የአበሻ ወሬ በአብዛኛው ከአዳም ይጀምራል፣ ቀረብ ሲል ከአድዋ፣ ካዘነልን ከአያቱ ይጀምራል፡፡ እኔም ተጋብቶብኝ ነው መሰለኝ እጽፋለሁ ብዬ የተነሳሁት ስለመልስ ጉዞዬ ነበር፡፡ የኔ ነገር፡፡ አውራ መንገዱን እለቅና በእግር መንገድ፤ በጀርባ ሰፈር ስዳክር እውላለሁ፡፡ በጣም አላዳክራችሁም ብዬ ልመን፡፡

ፈትለ የጓደኛዬ ባለቤት ልትጠይቀን ከአዲስ አበባ መጥታ ነበር፡፡ የአሜሪካንን የነፃነት በዓል (July 4th) ዕረፍት ወደ ሰሜን ካሊፎርኒያ ይዣት ሄድኩኝ፡፡ እኔ ያለሁበት ሎስ አንጀለስንም (Los Angeles) ጨምሮ ደቡብ ነው፡፡ በሰሜን ታዋቂ ከተማ ሣን ፍራንሲስኮ (San Fransisco) ነው፡፡ የካሊፎርኒያ ሬፑብሊክ ዋና ከተማ ሣክራሜንቶም (Sacramento) ያለው ሰሜን ነው፡፡ በስተቀር ቀሪው ትላልቆቹ ከተሞች ሣንታ ባርባራ (SANTA BARBRA) (SAN Dicgo) ሣን ዲያጎ፣ ሎስ አንጀለስ ሁሉ ያለው ደቡብ ነው፡፡

ካሊፎኒያ ከሌሎች ግዛቶች (States) የሚለይበት በከተሞቹ ሥም ነው፤ 90% ሥሙ የመልእክና የፃድቃን ሰማዕታት ስም ነው፡፡ የፃድቃኑና ሰማእቱ ይበዛል፡፡ LOS ANGELES ማለት መላእክቶች ማለት ነው፤ ኗሪው ራሱን ANGELINO ነኝ ይላል፡፡ መልአክ ነኝ እንደማለት ነው፡፡ እኔ አሁን አንጀሊኖ ነኝ፡፡

መላእክቱ የአይሁድ፣ የክርስትና፣ የእስልምና “የጋራ ንብረት” ናቸው፡፡ ፃድቃኑ የካቶሊኮቹ ናቸው፡፡ አገሩን ቅኝ ግዛት ያደረጉት /በአበሻ ያቀኑት ይባላል መሰለኝ/ እስፔይኖች የሰጡት ስም ነው፡፡ ቀማኛ ቀማኛ መጣና ካሊፎርኒያ አሜሪካ ሆነ፡፡ ባላአገሩን ነቀሉት፡፡ ፈጁት፡፡ ራሳቸውን ተክለው ለአገሩ የመላእክትና ሰማእታት ፃድቃን ስም ሰጡ፡፡ “ሥራ ክፉ በስም ይደግፉ” መሆኑ ነው መሰለኝ፡፡ በክርስቶስ ስም! ታላቁ የፈረንሳይ ፈላስፋ ቮልቴር፤ “…..Lhistoire des grandes eventments de ce monde n’est guere que l’historie des crimes…..” ያለውን አስታወሰኝ፡፡ የአለም ታላቁ ክንውኖች /ድርጊቶች/ የምንላቸው አብዛኛውን የወንጀል ታሪክ ናቸው ማለቱ ነው፡፡

የአሁኑ የሮማው ሊቃነ ጳጳሳት የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ ይመስለኛል፤ “ባለፈው 2000 ዓመታት ለፈፀምነው ደባ፣ ወንጀል ሕዝበ ክርስቲያን ይቅር እንድትሉን በተከታዮቹ ሁሉ ስም እጠይቃለሁ….” ብለው ነበር፡፡ ካሳ እከፍላለሁ አላሉም፡፡ ሆኖም ወንጀለኛነታቸውን ማመኑ “ክርስቲያናዊ” ይመስለኛል፡፡ የእኛዎችም የብረት መዝጊያ አጥረው “እሱ ነው! እሱ ነው!” እያሉ ዙሪያውን ከማካሰሱ …. የቀን ጉዳይ መሰለኝ!

CALIFORNIA መቼም የአውራ ጎዳና አገር ነው፡፡ FREEWAY ይሉታል፡፡ ነፃ ለማለት ነው፡፡ ከግብዎ በስተቀር የሚያቆምዎት የለም፤ ከአደጋ ይሠውርዎትና! ሎስ አንጀለስን The car Capital of the world ይሏታል፡፡ ዛሬ ይኼ እራሱ እራሱን የቻለ የሚጠና “ችግር” ሆኗል፡፡ ያው ጥናቱም ቀጥሏል፣ ቢጠና ቢጠና መፍትሄ አልተገኘም፡፡ “ወይ ሀብታም? መሆን? ያመጣው ጣጣ!” ብለው እያጉረመረሙ ይኖርዋታል፡፡ A necessary evil ከሚሉት ይመደባል፡፡ “ተፈላጊ ጣጣ!” እኔ እስቃለሁ፡፡ እንዴት ብዬ እንደማዝን ጠፍቶኝ ነው፡፡ እንዲህ ያለ ችግር ተምሬ እስክማረር ትንሽ ጊዜ መውሰዱ አይቀርም፡፡ ይህን ችግር ለማለት የአገሬን ችግር ሁሉ መርሳት ይኖርብኛል፡፡ እሱ ደግሞ አልጠፋም! አልረሳም አለን!!

በኪራይ መኪና መጓዙ ይቀላል፡፡ በዚህ ላይ ኪራዩ እርካሽ ነው፡፡ አሁን የተከራየሁትን መኪና ከአርብ እስከ እሮብ አቆይቼ 150 ዶላር ከፈልኩ፡፡ በ8 ብር አታባዙት /አትመንዝሩ/ እዚሁ ተገኝቶ እዚሁ የሚጠፋ ስለሆነ አንድን ዶላር አንድ ብር ማለቱ ይቀላል፡፡ መመንዘሩ አላስፈላጊ “እውቀት” ይናገራል፡፡ እኔ ከLos ANGELES እራቅ ብዬ በወጣሁ ቁጥር መኪና እከራያለሁ፡፡ አሁን ከፈትለ ጋር ወደ ሰሜን መጓዝ የጀመርነውን በኪራይ መኪና ነው፡፡

(ፈትለን ውቅያኖሱ ዳርቻ ወደብ ወሰድኳት) መውሰዴ የአሜሪካንን አንድ ትንሽ ከተማ እኔ በማየው መስኮት እንድታይ ብዬ ነው፡፡ ምድረ አለሙ፤ ህፃን፣ ሽማግሌ፣ አሮጊት፣ ጎልማሳ፣ ውሻ፣ ድመት ወጥቶ ይዝናናል፡፡ በተለይ ካሊፎርኒያ ትንሽም እረፍ ስትገኝ ሮጦ ወደ ተራራ መውጣት፣ ወደ ውቅያኖስ ዳርቻ መውረድ ነው፡፡ ከእነ ልጆቹ የልጅ ልጆቹ ወይ አሳ ያጠምዳል ወይ አሸዋ ላይ ይሰጣል፣ ወይ የሚበላውን ይጠባብሳል፣ ወይ ሆቴል ውስጥ ይበላል፣ ወይ ይተሻሻል፣ ወይ ይላላሳል… ምኑ ቅጡ! እንደ ፍጥርጥሩ!

አሜሪካ ከሰው ጋር የማውራት ችግር የለም፡፡ ከሀበሻው ጋር ካልሆነ በስተቀር፡፡ ጠጋ ብሎ Hi! ማለት ነው፡፡ ከዚያ ወሬውን ከጠርዙ ሳይሆን መሀል ገብቶ መቀርደድ ነው፡፡ ከየት መጣህ? የት ትሄዳለህ? ይህቺ ሚስቴ… ያ አባቴ…. ያኛውም …. አያቴ…. እነዛ የልጅ ልጆቼ….የምሰራው… መዘርዘር ነው፡፡ ትንሽ ካወሩ እኛ “ሚስጥር” የምንለውን ሁሉ አውጥቶ ይዘከዝካል፡፡ አሜሪካኖች እራሳቸውን ሀገራቸውንም “OPEN SOCIETY” ይሉታል፡፡ እውነታቸውን ነው፡፡ ብርግድ ብሎ የተከፈተ ነው፡፡ ለመግባባት በሩን ማወቅ ይፈልጋል፡፡

አሜሪካኖች ሌላ አንድ የሚያስቀናኝ ባህሪ አላቸው፡፡ በእንዲህ አይነቱ ቦታ አሁን ምን እየሰራህ ነው ሲባሉ አፋቸውን ሞልተው፤“I am having a Good Time!” ይላሉ፡፡ ትላንትና የት ነበርክ ሲሉት፤ “ I am having a Good Time!” ይላል፡፡ “እየተደሰትኩኝ ነኝ! ስደሰት ነበር!” እንዴት መታደል ነው፡፡ የእኛ ሰው አፉን ሞልቶ “እየተደሰትኩኝ ነኝ!” ሲል እስከ ዛሬ አልሰማሁም፡፡ እዚህም፡፡ ያለውም፣ የሌለውም፡፡ አንዳንዴ ለብቻዬ “እውነት ደስታ ማለት ምን እንደሆነ አናውቅ ይሆን” እላለሁ፡፡ ሀዘን እና ለቅሶ በዜማ ጭምር እንደምናውቅ አውቃለሁ፡፡

እዚህ ያለው ኢትዮጵያዊ በአብዛኛው አሜሪካንን ዞሮ አያይም፡፡ ቢያይም አያስተውልም፡፡ ይህን አይነት ጣጣ አያውቅም! ምን በወጣው! ተሰብስቦ ሲራኮቱ መዋሉን ትቶ! እንጀራ በወጥ ነው ቀለቡ፡፡ ውስኪ ኮኛክ ነው መጠጡ! ሙግት አደባባይ እርስ በርሱ ሲራኮት ነው የሚውለው- የሚያመሸው የሚያድረው፡፡ ጋዜጣ አያነብብም፡፡ ለመፅሄቶች Subscribe አያደርግም! Art… exhibition አይሄድም፡፡ የቤተ መፅሀፍት አባል አይደለም…. እንዴት ሊያውቅ ይችላል!

አንድ ሁለት አመት East coast ነበርኩ፡፡ D.C ዛሬ እሁድ የት ዋልክ? ይሉኛል፡፡ While House, Library of Congress, Capitol,… እላለሁ፡፡ ባለፈው ሳምንት ሄደህ አልነበር? ይሉኛል፡፡ አንዴ አይበቃም ወይ? ነው፡፡ ዘመናት ኖረው While House Congress ስብሰባ ላይ ሆነው ያላዩ ማስተዋል ምንድነው የምታየው /የሚታየው? ይሉኛል፡፡

“The Power Corriitdor” አያለሁ ብል አበቃ፡፡ “ቀጥቃጭ አይደለሁም! ቢሆንማ መልሱ?” አይነት ነው፡፡ ይህ እኮ ቦታ ይህ መላውን አለም የሚያንቀጠቅጠው የሚያቦካው፣ የሚጋግረው… የሚከፍለው…. የሚነቅለው …ያድራጊው የፈጣሪው… መቀመጫ ነው! ይህን ድርሃ ፂዮን… ይህንን እየሩሳሌም ደጋግሜ መሳለሜ ቢያንስ እንጂ ሲበዛ አይደለም፡፡ ሌላው ቢቀር ማድነቅ መዳነቅ መገረም ማሽተት ያቅታል! ብል ማን ሰምቶኝ፡፡

Addis Admass

10 Jan, 19:55


ፈትለን አሜሪካን በመስኮት ካሳየኋት በኋላ ጉዞ ቀጠልን፡፡ ይህንን የካሊፎርኒያ አካባቢ በጣም የምወደው ነው፡፡ መንገዱ ተራሮችን ቀዶ፤ ኮረብታዎችን ሰንጥቆ ወይ ወደጎን እና ጎን ትቶ፤ ረጃጅም ሸለቆዎችን ወርዶ፤ ረጃጅም በግርማ የሚጥመለመሉ አቀበቶችን ወጥቶ አቋርጦ የሚሄድ ነው፡፡ ይህ ገፀ ምድር (Land scape) ሰአሊዎች እውቆቹ ጭምር ምን ያህል ተፈጥሮን ለመቅዳት ሞክረው እንዳልተሳካላቸው ያም ያልተሳካላቸው እንደተደነቀላቸው ለማነፃፀር ከሣን ሊውስ ኦቢስፖ ወደ ላይ በSANTA MARIA, በSAN MIGUEL, በMONTERY, በSALINAS አድርጎ መጓዝ ነው፡፡
ሀገሬን ያስታውሰኛል፡፡ ትዝታ ይቀሰቅስብኛል፡፡ ከእንጦጦ ቁልቁል ወደ ስላሴ ወደ አባይ ሸለቆ ስወርድ ወደ ደጀን ስወጣ ይታየኛል፡፡ በልጅነት በእግሬ ከጨንቻ ወደ ምእራብ “ወደ አባቴ አገር” ስሄድ የወጣኋቸው የወረድኳቸው ተራሮች ኮረብቶች ሸለቆ ይታዩኛል፡፡ የኢሌ ገብርኤል መሳለሚያ ውሎ ቆዴ ቆሞ ከማዶ የገብርኤል ቆርቆሮ ክዳን ብልጭ ድርግም የሚለውን በጭጋግ የተሸፈነውን እና ደጀን ሆኖ የቆመው ዋጉጌ ተራራ ይታየኛል፡፡

ትዝታ ነው የሚርበኝ፣
ላናገኘው ላያጠግበን
የሚለውም ይመጣል፡፡ ፈትለ እና እኔ በዚህ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ውበት ብዙም ሳናወራ ተጓዝን፤ አልፎ አልፎ አንዳንድ የአድናቆት ቃላት ወይም አረፍተ ነገር እንለዋወጣለን፡፡ ገጣሚ በአንዲት ስንኝ ቋጠሮ ብቃት ባለው ስሜት እንደሚገልፀው ይመስለኛል፡፡

ካሊፎርኒያ ባብዛኛው ውሃ የሌለው በርሃ ነው፡፡ እኔ እስከዛሬ ወንዝ አላየሁም፡፡ እዚህ አጠገቤ Los ANGELES River የሚሉት ትልቁ ቀልድ አለ፡፡ በሲሚንቶ የተሰራ ትልቁ ፍሳሽ ጎርፍ የሚወርድበት ሰው ሰራሽ ወንዝ ነው፡፡ ታዲያ ውሃው ከየት መጣ ማለት ጥሩም ተገቢም ጥያቄ ነው፡፡ ውሃው የሚመጣው ከCOLORADO ወንዝ ነው፡፡ የኮሎራዶ ወንዝ የሚገኘው ከእኛ አንድ ግዛት አልፎ ነው፡፡ NEVADA አልፎ ነው፡፡ ከ500 ማይልስ ነው፡፡ ከ900 ኪሎ ሜትር ነው፡፡

ካሊፎርኒያ በአብዛኛው የኤሌክትሪክ ሀይሏንም የምታገኘው ከኮሎራዶ ነው፡፡ በደቡብ በኩል ጎረቤት ክልል Orange county ይባላል፤ የብርቱካን ክፍለ ሀገር እንደማለት ነው፡፡ ሩዝ ለጃፓን ጭምር ሳይቀር ይሸጣል፡፡ ቡና ለኢትዮጵያ እንዳይልክ ያሰኛል፡፡ ይህ ካሊፎርኒያ በአለም 8ኛ ሀብታም ሀገር ያደረገው የእርሻ ታምር በግዢ 900 ኪ.ሜ ተጉዞ፣ ተስቦ የመጣ ውሃ ነው፡፡

ሀገሬ እንደገናም ትዝ ይለኛል፤ ወንዞቿ ሁሉ ትዝ ይሉኛል፤ አዋሽ ይታየኛል፡፡ ወይም ወንዞቹን ወክሎ በፀጋዬ በኩል አዋሽ ያለው ትዝ ይለኛል፡፡
…ከከረዩ መተሀራ ከአኋቱ እስከ አፋር አምጦ
አሸዋ ነክሶ ቀረ አዋሽ ሳይገላገል ሸምጥጦ
እንደወላድ ሳይታረስ ከነፅንሱ በረሃ ሰምጦ
በምድረ በዳ ጉሮሮ በረሃ ላንቃ ተውጦ
እስከ መቼ ይሆን አዋሽ… ?

“አዋሽ ነክሶ ቀረ አዋሽ ሳይገላገል አምጦ” በብርቱ ያሳስበኛል፡፡ ከዚህ ሁሉ የሰበሰበውን ሀብት ሰብስቦ አዋሽ መቀመቅ ይከታል፡፡ የታደሉት ከ900 ኪ.ሜ ውሃ ይስባሉ፡፡ “ይታደሉዋል እንጂ ….” ሊባል ይሆን?

እሺ ባለቤቴ
“ያለው ማማሩ
የሌለው መደበሩ!” ትላለች፡፡
***

(አዲስ አድማስ፤ ጥር 20 ቀን 1992 ዓ.ም) ⬇️⬇️

Addis Admass

10 Jan, 19:33


አዲስ አድማስን ለብዙ ዓመታት አንብቤአለሁ፤ ወደፊትም አነባለሁ፡፡ ጋዜጣውን እንዳገኘሁ መጀመሪያ የማነበው የነቢይ መኮንንን (ነፍሱን ይማረውና) ርዕስ አንቀጽ ነው፤ ሁለተኛ የማነበው ደግሞ የዮሐንስ ሰ.ን ጽሁፍ ነው፡፡ እኔ ከልጆቹ ቀድሜ ካነበብኩ ጥሩ የምላቸውን ጽሁፎች እንዲያነቡ እጠቁማቸዋለሁ፡፡ ሁሉም አምዶች ሳምንቱን ሙሉ የሚነበቡ ናቸው፡፡ በእኔ በኩል፣ አዲስ አድማስን በድረ ገፅ አላነብም፤ለዕድሜዬ አይሆንም፤ በዚያ ላይ ጋዜጣው ሁሌም በእጄ ነው።

በአዲስ አድማስ ላይ በርካታ አስገራሚና አስደማሚ ታሪኮችን አንብቤአለሁ፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱና ሁሌም የማይረሳኝ፣ ኮፊ አናን ኢትዮጵያ በነበሩ ጊዜ የቤት ውስጥ ረዳታቸው የነበሩትን ሴት ተመልሰው ሲመጡ ሊያገኟቸው ፈልገው፣ ሴትየዋ በቀጠሮው ሰዓት ባለመድረሳቸው ሳይገናኙ መቅረታቸውን የሚያትተው ታሪክ ነው፡፡ የቀጠሮ ሰዓት የማያከብር ሰው ስለሚገርመኝ ይሆናል፣ ይሄ ታሪክ ሁሌም ትዝ የሚለኝ፡፡

በእርግጥ የማነበው ጋዜጣ ብቻ አይደለም፤ መፅሔቶች የታሪክና የሀይማኖት መጻሕፍትንም አነባለሁ፡፡ ዜናም አያመልጠኝም፡፡ ማንበብ ብዙ ጠቀሜታዎች አሉት፡፡ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ዕውቀትን ያስታጥቃል፡፡ መረጃን ከሰው አፍ ከመስማት አንብቦ መረዳት የተሻለ ነው፡፡

የአዲስ አድማስ ፀሐፊዎችና አዘጋጆች፣ ከአንባቢዎቻቸው ቀድመው መገኘት አለባቸው፤ በሁሉም ረገድ ሊበረቱ ይገባል፡፡ ጋዜጣው አምዶቹን መጨመር እንጂ መቀነስ የለበትም፤ የተቀነሱ አምዶች ስላሉ የጎደሉትን ማሟላት ያስፈልጋል፡፡ በመጨረሻ እንኳንም ለአዲስ አድማስ 25ኛ ዓመት አደረሳችሁ እላለሁ፡፡ መልካም የሥራ ዘመን ይሁንላችሁ።

Addis Admass

10 Jan, 19:29


“ሁሉም አምዶች ሳምንቱን ሙሉ የሚነበቡ ናቸው”


ወይዘሮ ፈለቀች ለማ እባላለሁ፡፡ የቤተሰብ አስተዳዳሪና የአስራ አንድ ልጆች እናት ነኝ፡፡ በጥሩ ቤተሰብ ውስጥ ነው ያደግሁት፡፡ ትምህርት የጀመርኩት በቄስ ትምህርት ቤት ነው፤ ከዚያም በመንግሥት ትምህርት ቤት ገብቼ እስከ ስድስተኛ ክፍል ከተማርኩ በኋላ በሀገሩ ባህልና ወግ መሠረት በጣም በልጅነቴ ተዳርኩ፡፡ ሆኖም ያኔ ሲንጀር ካምፓኒ የሚሰጠውን የዲዛይን ትምህርት ጨርሼ ከተመረቅሁ በኋላ፣ በጅማ የሴቶች በጎ አድራጎት ድርጅት፣ ከጓደኞቼ ጋር በመሆን፣ ሴቶች ራሳቸውን እንዲችሉ፣ የልብስ ስፌትና ጥልፍ ስልጠና በመስጠት እናስመርቅ ነበር።

አዲስ አድማስ ከመጀመሩ በፊት ባለቤቴ ሁሌም ጋዜጣና መፅሔት እንዲሁም መጻሕፍት እየገዛ ያመጣ ስለነበር፣ ንባብ የቤታችን ባህል ሆኗል፡፡ በኋላም አዲስ አድማስ ቅዳሜ መውጣት ሲጀምር ልጆቹም በዚያው ቀጠሉበት፡፡ እኔም ጋዜጣውን ማምጣት እንዳይረሱ ሁሌም አስታውሳቸዋለሁ፤ በጣም የሚወደድ ጋዜጣ ስለሆነ ምንጊዜም እንዲያልፈኝ አልፈልግም፡፡

Addis Admass

08 Jan, 21:12


Here's a highly reliable online part-time job platform that I would like to recommend to you: BTT.

BTT is one of the largest advertising networks globally and is currently recruiting online part-time employees in Ethiopia.

No academic qualifications or work experience are required, and you can easily start earning money with just a smartphone. By downloading the designated app and increasing the download rate of other companies, you can earn lucrative referral fees.

💸 Daily income up to 4,000 ETB
📱Simple operation, only 15-20 minutes per day
Free without any investment
📈 Provides exclusive training to help you

If you are interested in this opportunity
please click the BTT official channel to contact customer service:
https://t.me/+fKeyX9Wh95wxMWNl

Addis Admass

08 Jan, 19:10


የቤንዚን ዋጋ ከ10 ብር በላይ ጨምሯል። በተደጋጋሚ እንደተገለጸውም የዋጋ ንረት አዙሪቱ ቀጥሏል፣ ገና ይቀጥላል።
ታህሳስ 22 ቀን 2017 የገንዘብ ፓሊሲ ኮሚቴ ገጽ 2 ላይ ባቀረበው ዓለም አቀፍ ሁኔታዎች ግምገማ መሰረት በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ 15% ቀንሷል። ቡናና ወርቅ ዋጋ በመጨመሩ የውጭ ክፍያ ሚዛንም ተሻሽሏል።
የነዳጅ ዋጋ እየጨመረ ያለው በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩና የመንግስት የውጭ ክፍያ ሚዛን በመዳከሙ ምክንያት እንዳልሆነ ሪፖርቱ ግልጽ አድርጎልናል።
ይህ ማለት የነዳጅ ዋጋ የጨመረበት ምክንያቱ የብር የመግዛት አቅም እንዲዳከም በመደረጉ እንጂ ዓለም አቀፍ የነዳጅ ዋጋ በመጨመሩ እንዳልሆነ ያመላከተ ነው። እንደዚህ ዓይነቱ አዙሪት መቆምያ ጠገግ እንደሌለውም ሂደቱ ገላጭ ነው።
የብር የመግዛት አቅም ሲዳከም ኢኮኖሚው ውስጥ ያልነበረ ተጨማሪ ብር እንዲፈጠር ግድ ይላል። ምርትና ምርታማነትን ተከትሎ ያልተፈጠረ ብዙ ብር ከጥቂት ምርት ጋር ሲጋፈጥ ዋጋ ንረት መከተሉ የማይቀር ነው።
የዋጋ መናር የገንዘብ የመግዛት አቅምን ያዳክማል። የብር የመግዛት አቅም መዳከም የውጭ ምንዛሪ አቅምን ያንራል። የውጭ ምንዛሪ አቅም መናር ደግሞ የዋጋ ውድነትን ያስከትላል። የውጭ ምንዛሪ አቻ ትመና መናር የብር የመግዛት አቅምን ይዳከማል።
የብር መግዛት አቅም መዳከም የዋጋ ንረት፣ የዋጋ ንረት ተጨማሪ የብር ፍላጎት፣ ተጨማሪ የብር ፍላጎት ተጨማሪ ብር መፈጠርን፣ የብር መብዛት የገንዘብ ግሽበትና የዋጋ ንረትን ያስከትላል። አዙሪቱ ይቀጥላል።

Addis Admass

07 Jan, 20:51


ይህንን ሙሉ ስነ-ስርዓት በየአመቱ በአካል ለመታደም ወደ ጉራጌ አካባቢ ከ120 እስከ 150 ኪሎ ሜትሮች ብቻ በመጓዝ ያገኙታል።
ይምጡ ይጎብኙ፤ በሃገር በቀል ባህሎቻችን ይዝናኑ!
☀️☀️☀️
ማኛም በኬር አሰላንኽም- እንኳን አደረሳችሁ!
Photo credit: ደቡብ ሶዶ ወረዳ ኮሙኒኬሽን🙏 ሶዶ ለማ-Sodo Lema

Addis Admass

07 Jan, 20:48


''ኢምር ኢምር ቦግ ቤል...ኢምር ቦግ ቤል
ዬዳኮኛ ኧቡር ተክ ቤል''...እያሉ ይጫወታሉ።
''ፀሀይ ሆይ ፈካ በይ
የእናታችን ጠላት ዱብ በይ'' እንደማለት ነው።
ከዚሁ ጎንለጎን በሰፊ መስክ(አንቃት) ሲጫወቱ ያረፋፈዱት ወንዶቹ ደግሞ የገና ዱላቸውን ከፍ አድርገው ''እንዞሪቴ'' የተሰኘውን ጨዋታ እየጨፈሩ ወደ መንደር ይመጣሉ። ክዋኔው ስፖርትም ሊባል ይችላል።
''ዬ ዬ እንዞሪቴ ገና ነበቦ
ምድር ሰማይ ጠበቦ''
:
ጌታችን በመወለዱ ደስታ በምድር መብዛቱን ለማመላከት የሚዘፈን ነው።
በሌላ በኩል፦
''ዬገኒ ባልዎልደ የገኒ ባልዎልደ
ያብሽን ዬጎሽ ዎልደ!''
:
እያሉ የሚጫወቱት ጭፈራም የበዓሉ ሌላ ድምቀት ነው። ጌታችን እየሱስ ክርስቶስ ከፈጠራት በኋላ መርጦ ዳግም ከተፈጠረባት እናቱ ድንግል ማርያም የተገኘና የአለም መድኀኒት ሲሆን በልደት በዓሉ ወቅት የገና ልጆች የሚያዜሙላት አንዲት እናትም በየአመቱ ወንድ ልጅ እንዲሰጣት የሚመርቁበት ባሕላዊ ይዘት ያለው ጨዋታ ነው።
በሶዶ ክስታኔ-በጉራጌ በዚህ መልኩ በሚኳሸው የገና በዓል ሴቶች በተለይም በቅርቡ ወንድ የወለደች እናት ካለች ለወጣቶቹ ድፎ ዳቦ ታቀርብላቸዋለች። አባዎራዎች ደግሞ እንደየአቅማቸው(ያለው አርዶ የሌለው በቅርጫ ስጋ) ቤቱን አሟሙቀው ለብሰው ታቦት ለማንገስ ወደ ቤተክርስቲያን ይጓዛሉ። እዚያ ሁሉም ይሰባሰባሉ። ጭፈራው ፈረስ ጉጉሱ ይደራል።

Addis Admass

07 Jan, 20:48


''ኢምር...ኢምር'' የገና በዓል ጨዋታ በሶዶ ክስታኔ ቤተ-ጉራጌ
☀️☀️☀️
በጉራጌ የራሳቸው የሆነ ደማቅ መልክ ካላቸው በአላት መካከል(ከመስቀል ቀጥሎ) አንዱ ገና ነው። በሶዶ ክስታኔ ቤተ-ጉራጌ የገና በዓል አካባቢያዊ ትውፊታዊ ክዋኔ አለው።
እለቱ እስኪደርስ ወንዶች የገና ዱላቸውን ከማዘጋጀት በዘለለ የእንጨት ፈለጣ ስራቸውንም ጠንቅቀው ያከናውናሉ። ሴቶችም የዶሮ አይን የመሰለ ጠላ፣ በቅቤ የታሸ ቆሎና ድፎ ዳቦ በውርርድ ያዘጋጃሉ።
እለተ-ገና በማለዳው ቀሚስ ለባሽ ልጃገረዶች ''ኤጎስቴ''(ጓዴ/አብሮ አደጌ ማለት ነው) እያሉ ተጠራርተው ከበሮ፣ ጠላ እና ቆሎ ይዘው ይሰባሰባሉ። ከምትፈነጥቀው ፀሃይ ግባት(ጮራ) ጋር ጥብቅ ንግግርም አላቸው። ''የገና ጀንበር'' አድማቂ ናቸው።
የናፍቆት ሰላምታና ዝግጅታቸውን ከጨረሱ በኋላ ወደ ምስራቅ ዞረው እግራቸውን ዘርግተው በመደዳ ይቀመጣሉ። ከቻሉ በቁጥራቸው ልክ ወንፊት ይይዛሉ። ካልቻሉም በእድሜ ታላቋ ትይዛለች።
ቀጣዩ ተግባር ፀሃይዋን በወንፊቱ ቀዳዳ እያዩ ''ኢምር ኢምር #አት...ኢምር ኢምር #ኪት '' እያሉ እስከ 12 መቁጠር ነው። ይህም እየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም ሲወለድ ወርቅ፣ ከርቤ እና እጣን በእጅ መንሻነት ይዘው በኮከብ እየተመሩ ከምስራቅ የመጡትን ''ሰብአ-ሰገል'' የሚያስታውስ ነው።
ልጃገረዶቹ ይህንን ካደረጉ በኋላ ቆሎው፣ ጠላው እና ዳቦውን ከወንፊቱ ስር አድርገው፦

Addis Admass

07 Jan, 20:37


በላሊበላ ከተማ የገና በዓል በድምቀት ተከበረ
በላሊበላ ከተማ የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል (ገና) ከዋዜማው ጀምሮ ሃይማኖታዊ ስርዓቱን ጠብቆ በድምቀት ተከበረ።
ዛሬ በተጠናቀቀው በዓል ላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ቱሪስቶች የታደሙ ሲሆን፤ ሂደቱም የተሳካና ላሊበላ ከተማን ያደመቀ እንደነበር ተነግሯል።
በዓሉ በድምቀትና በስኬት እንዲጠናቀቅ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፀጥታ አስከባሪዎች ጋር በመሆን በጋራ በመስራት አስተዋጽኦ አድርገዋል።
በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ነጋ ድንበሩ እንደገለጹት፤ ሥነ-ሥርዓት በማስከበር የበዓል ማክበር ሂደቱ የተሳካ እንዲሆን ማደረግ ተችሏል።
ታዳሚዎች በዓሉን ያለምንም ችግር ማክበር እንዲችሉ የፀጥታ ሃይሉ ወጣቶችን ያሳተፈ ወንጀልን የመከላከልና ሰላም የማስክበር ስራ ማከናወኑን ተናግረዋል።
ለዚህም ከዋዜማው ጀምሮ በተከናወነ የተቀናጀ ስራ በዓሉ በድምቀትና በስኬት ተከብሯል ብለዋል።
በበዓል አከባበሩ በተራ ሌብነት ተሰማርተው የተገኙ ሦስት ግልሰቦች መያዛቸውንና በጊዜያዊነት ለተቋቋመው ችሎች ቀርበው ውሳኔ እንዲያገኙ መደረጉን መግለጻቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

Addis Admass

07 Jan, 20:11


ጤና ሚኒስቴር ለመቄዶኒያ የአምቡላስ፣ 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የመድሃኒትና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ
**************
ጤና ሚኒስቴር የገናን በዓል ምክንያት በማድረግ ለመቄዶኒያ በጎ አድራጎት ማህበር የአምቡላስ እንዲሁም 4 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የመድኃኒት እና ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።
የጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ እና ሌሎችም የተቋሙ የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት የገና በዓልን ምክንያት በመቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር ለሚኖሩ ወገኖች ማዕድ አጋርተዋል።
የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ በዚሁ ወቅት፥ የጤና ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት ማህበሩ ላስጠለላቸው ወገኖች የሚውሉ የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን አስታውሰው፤ በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጠዋል።
ከዚህ በፊት የመድኃኒት፣ የአምቡላንስና ሌሎችም ድጋፎች ሲያደረጉ እንደነበር አንስተው፤ በቀጣይም ድጋፉን ያጠናክራል ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል።
የመቄዶኒያ የበጎ አድራጎት ማህበር መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ ቢኒያም በለጠ በበኩላቸው፥ በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በ44 ቅርንጫፎች ከ8 ሺህ በላይ ወገኖችን እየደገፈ መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣይ የሚደግፋቸውን ወገኖች ቁጥር 20 ሺህ የማድረስ ዕቅድ እንዳለው ገልፀው፤ ማህበሩ በ15 ከተሞች የቅርንጫፍ ማዕከላት ግንባታ እያካሄደ መሆኑን ተናግረዋል።

Addis Admass

07 Jan, 19:35


በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ሚኒስቴሩ ይፋ ባደረገው መረጃ መሰረት ከዛሬ ታኅሣሥ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ተግባራዊ የሚሆን የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ እንደሚከተለው ሆኖ ተወስኗል።
1 አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር፣
2 አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር፣
3 አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር፣
4 አንድ ሊትር የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር፣
5 አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር እንዲሁም
6 አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር ሆኖ እንዲሸጥ ሚኒስቴሩ ወስኗል።

Addis Admass

06 Jan, 20:37


"የቀይ ባሕርን ዳርቻ መጠቀም የሚችሉት ከባሕሩ ጋር የሚዋሰኑ አገራት ብቻ መኾን አለባቸው"

የግብጹ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ፣ የቀይ ባሕርን ዳርቻ መጠቀም የሚችሉት ከባሕሩ ጋር የሚዋሰኑ አገራት ብቻ መኾን አለባቸው በማለት ትናንት ከሱማሊያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሕመድ ፊቂ ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ መናገራቸውን የግብጽ ዜና ምንጮች ዘግበዋል።

የቀይ ባሕር ዳርቻ፣ አዋሳኝ ላልኾኑ አገሮች ክፍት ሊኾን እንደማይችል አብደላቲ ገልጸዋል ተብሏል። አብደላቲ ይህን ያሉት፣ ሱማሊያ ለኢትዮጵያ የባሕር በር ለመስጠት በምትችልበት ኹኔታ ዙሪያ በቀጣዩ የካቲት የቴክኒክ ንግግር ለመጀመር ኹለቱ አገሮች በተስማሙ ማግስት ነው።

ሁለቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች፣ የሱማሊያ ፌደራል መንግሥት በኹሉም የአገሪቱ ግዛቶች ሙሉ ቁጥጥሩን ማስፈን በሚችልበት ኹኔታ ዙሪያ እንደመከሩም አብደላቲ በመግለጫው ላይ ጠቅሰዋል። ኹለቱ አገራት ግንኙነታቸውን ወደ "ስትራቴጂካዊ አጋርነት" ለማሸጋገር መስማማታቸውን የገለጡት ደሞ የሱማሊያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፊቂ ናቸው።

(ዋዜማ ሬዲዮ)

Addis Admass

06 Jan, 20:29


https://rb.gy/m2tydd
(ለትውስታ)

Addis Admass

06 Jan, 18:06


ኢትዮፒካር
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የልደት በዓል እንዲሆንላችሁ ይመኛል።

Addis Admass

06 Jan, 17:37


እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረስዎ! በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣
የፍቅርና የደስታ እንዲሆንልዎ እመኛለሁ!

Addis Admass

06 Jan, 16:52


የአእላፋት ዝማሬ

Addis Admass

06 Jan, 08:17


የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ከማዕከል እስከ ወረዳ ከ400 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ በዝቅተኛ ገቢ ለሚተዳደሩ እና የኑሮ ጫና ላለባቸው የከተማችን ነዋሪዎች ማዕድ አጋርተናል።
እንዲህ ያሉ የህብረተሰቡን የኑሮ ጫና የሚያቀሉ ስራዎችን እንድንሰራ፣ “መስጠት አያጎድልም” ብለው ከጎናችን በመቆም ጉልበት የሆኑንን የከተማችን ባለሀብቶች በነዋሪዎቻችን ስም ላመሰግናቸው እወዳለሁ።
መልካም በዓል!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

Addis Admass

04 Jan, 21:46


Hello everyone! 🌟 I'd like to introduce you all to a lucrative job opportunity.

BTT is one of the largest advertising networks globally, and it is currently hiring online part-time employees in Ethiopia. 🌍

No academic qualifications or work experience are necessary – just a smartphone is all you need to get started.

📱 By downloading a designated app and boosting the download rates of other companies, you can easily begin to earn money! 💸

💰 Income Security: You can earn up to 25,000 ETB daily. With daily settlements and real-time withdrawals, your income is more secure than ever!

🌟 Key Advantages:- Zero Threshold: No professional skills required.- Safe and Reliable: All apps are rigorously selected to ensure information is secure!- Flexible Scheduling: Participate anytime that suits you.

📢 Limited-time Benefit: The first 100 joiners will have the chance to receive a reward of 5,000 ETB! 🎉 ⬇️⬇️

Addis Admass

04 Jan, 21:46


Join the official BTT channel, contact the customer service within the channel to register, and start earning money today! 💼🚀

https://t.me/+u5l252_cZTVmNmNl

Addis Admass

04 Jan, 20:49


"ለአካል ጉዳተኞች እና ዕድሜያቸው ለገፋ ሰዎች የሚያገልግል ዊልቸር ዕጥረት ተፈጥሮብኛል" ያለው ድርጅቱ፣ በጎ ፈቃደኛ የሆኑ ግለሰቦች፤ በተለይም ከዚህ ቀደም ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ ባለሃብቶች ቃላቸውን ተግባር ላይ እንዲያውሉ ጠይቋል። የድርጅቱ የገቢ ምንጭ በአብዛኛው ከአባሎች በሚገኝ መዋጮ፣ በድርጅቱ ስር ካለው ትምሕርት ቤት እና በባሕር ዳር ከተማ ከከፈተው የፍራፍሬ ጭማቂ መሸጫ ቤት የሚመነጭ በመሆኑ፣ በስሩ ለሚገኙ 50 ቋሚ ሰራተኞች ደመወዝ ከመክፈል እና በማዕከሉ ላሉ ድጋፍ የሚሹ ወገኖች ድጋፍ ከማድረግ በዘለለ መጠነ ሰፊ ስራዎችን እንዳይሰራ ተግዳሮት እንደሆኑበት ጠቁሟል።

ዝግባ የሕጻናትና አረጋውያን መርጃ የበጎ አድራጎት ድርጅት 16ኛ ዓመት የምስረታ ክብረ በዓሉን ለማክበር መዘጋጀቱን በመጠቆም፣ ገቢ ከማሰባሰብ በተጨማሪ የመገናኛ ብዙሃን ትኩረታቸውን ለድርጅቱ እንዲያውሉ ዕንቅስቃሴ እንደሚያደርግ አብራርቷል።

Addis Admass

04 Jan, 20:49


ወቅታዊው የጸጥታ መደፍረስና የኑሮ ውድነት ፈተና እንደሆኑበት
ዝግባ የሕጻናትና አረጋውያን መርጃ የበጎ አድራጎት ድርጅት አስታወቀ


ከተመሰረተ 16 ዓመታትን ያስቆጠረው ዝግባ የሕጻናትና አረጋውያን መርጃ የበጎ አድራጎት ድርጅት፤ በአማራ ክልል የተፈጠረው የጸጥታ መደፍረስና የኑሮ ውድነት ፈተና እንደሆኑበት አስታውቋል። ድርጅቱ የምስረታ ክብረ በዓሉን ለማክበር በዝግጅት ላይ መሆኑንም ገልጿል።

ባለፈው ሐሙስ ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም. በጌትፋም ሆቴል በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ የድርጅቱ ሃላፊዎችና የበጎ ፈቃድ አምባሳደሮች የተገኙ ሲሆን፣ ስለድርጅቱ ዝርዝር ማብራሪያ አቅርበዋል። በማብራሪያቸውም ላይ ድርጅቱ ዋና መቀመጫውን በባሕር ዳር ከተማ በማድረግ ከ2 ሺሕ 650 በላይ ወላጆቻቸውን በሞት ላጡና ለከፋ ችግር የተጋለጡ ሕፃናትና ጧሪ አልባ የሆኑ አረጋውያን በመደገፍ፣ እንዲሁም ችግረኛ ሴቶችን በገቢ ማስገኛ ስራ በማሰማራት ኑሯቸውን እንዲያደላድሉ ማስቻሉን የድርጅቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ስለሺ ጌታቸው አመልክተዋል።

በ27 በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦች የተቋቋመው ይህ የበጎ አድራጎት ድርጀት፣ የራሱ ተሽከረካሪዎች እንደሌሉት፤ የቦታ ጥበት እንዳለበት፤ የከርሰ ምድር ውሃ ችግር ስለመኖሩ በዚሁ መግለጫ ተነግሯል። ከዚህም ባለፈ በአማራ ክልል የተፈጠረውን የጸጥታ መደፍረስና የኑሮ ውድነቱን ተከትሎ፣ የተፈጠረው የፍጆታ ዕቃዎች አቅርቦት ዕጥረት "እየፈተነኝ ነው" ሲል ድርጅቱ አስረድቷል።

⬇️

Addis Admass

04 Jan, 20:48


ዓለምፍሬ ፒንክሃውስ ካንሰር ፋውንዴሽን የድጋፍ ጥሪ አቀረበ

ዓለምፍሬ ፒንክሃውስ ካንሰር ፋውንዴሽን ለመላ ኢትዮጵያውያን የድጋፍ ጥሪ አቅርቧል። ፋውንዴሽኑ በተደጋጋሚ የመሬት ጥያቄ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጥያቄ ቢያቀርብም፣ ምላሽ እንዳላገኘ አመልክቷል።

ባለፈው ዓርብ ታሕሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም. በግዮን ሆቴል ሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ ፋውንዴሽኑ በዶክተር ፍሬሕይወት ደርሶ ከአስራ ሶስት ዓመታት በፊት በአሜሪካ አትላንታ እንደተመሰረተ በማውሳት፣ በካንሰር ሕመም ላይ ቅድመ መከላከል የግንዛቤ መስጠት ስራ ሲሰራ መቆየቱ ተብራርቷል። በአዲስ አበባ እና ጎንደር ከተሞች ከ8 ሺሕ በላይ የካንሰር ታማሚዎችን የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ እያደረገ የሚገኝ ድርጅት መሆኑም ተገልጿል።

የድርጅቱ የቦርድ አባል ወይዘሮ ጸዳለ ጽጌ እንዳስታወቁት፣ ፋውንዴሽኑ በዓመት ሁለት ጊዜ በካንሰር ሕመም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ኮንፈረንስ ያዘጋጃል። አክለውም፣ በሁለተኛው ኮንፈረንስ አማካይነት በሕመሙ የተጠቁ ወገኖች እርስ በርሳቸው የውይይት መድረክ እንደሚያካሂዱ አስረድተዋል።

"የካንሰር ታማሚዎች ጤና የእርስዎም፣ የእኔም፣ የሁላችንም ጉዳይ ነው" የሚለው ፋውንዴሽኑ፣ መላ ኢትዮጵያውያን የድጋፍ እጃቸውን እንዲዘረጉ ጠይቋል። አሁን ላይ እየሰራቸው ካሉ ስራዎች በተጨማሪ፣ በቀጣይ ሌሎች በርካታ ዕንቅስቃሴዎችን ለማድረግ የተለያዩ ዕቅዶችን እንደነደፈ ተነግሯል።

Addis Admass

04 Jan, 20:44


በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተብራራው፤ የበጎ አድራገት ድርጅቱ አምስተኛ ዓመት በዚሁ ማዕከል ከባቡል ኸይር ቤተሰብና አረጋዊያን ጋር አብሮ በማሳለፍና በጉብኝት ይከበራል፡፡

የድርጅቱ አጋርና ደጋፊ እንዲሁም የበዓሉ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል ወጣቱ ባለጸጋ ምህረትአብ ሙሉጌታ ባደረገው ንግግር፤ “ባቡልኸይር ራሱን በራሱ ለመርዳት መንግስት በሰጠው መሬት ላይ ትልቅ ህንጻ ለመገንባት የጀመረው አካሄድ ይበል የሚያሠኝና የእኛን ድጋፍ የሚሻ በመሆኑ ደጋግ ኢትዮጵያውያን በቻላችሁት አቅም በማገዝ አሻራችሁን ልታሥቀምጡ ይገባል።” ብሏል፡፡

በተጨማሪም ለ5ኛ አመት ክብረ በአሉም ሁላችንም ተገኝተን የቻልነውን እናግዝ ሲል ጥሪ አስተላልፏል።

126 ሰዎችን በመመገብ የበጎ አድራጎት ሥራውን ሀ ብሎ የጀመረው ባቡል ኸይር፤ ዛሬ ላይ ከ5 ሺህ በላይ ችግረኛ ወገኖችን በቀን ሁለት ጊዜ ምሳና እራት እየመገበ የሚገኝ ሲሆን፤ የጤና መድህናቸውንም ማረጋገጥ ችሏል ተብሏል፡፡

በርካታ ቁጥር ያላቸውን ወጣቶችና ሴቶችን በተለያዩ ሙያዎች (ልብስ ስፌት፣ የኮምፒዩተር ስልጠና፣ የጫማ ስራ) እያሰለጠነና የስራ እድሎችን ጭምር እያመቻቸ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡


ዛሬ ላይ ባቡል ኸይር በአበበ ቢቂላ የመመገቢያ ማዕከልና የሙያ ስልጠና ማሳያ ስፍራ፣ በአቃቂ ቃሊቲ የስልጠና ማዕከልና የህፃናት ማቋያ ያለው ሲሆን፤ በኦሎንኮሚ ለወጣቶች የስራ እድልን እየፈጠረ የሚገኝ የብሎኬት ፕሮጀክት ግንባታ እያከናወነ ይገኛል።

Addis Admass

04 Jan, 20:44


ባቡል ኸይር በ1.2 ቢ.ብር የአረጋውያን መጠለያ
ሁለገብ ማዕከል ሊያስገነባ ነው


• ለግንባታው እውን መሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ድጋፍ
እንዲያደርግ ተጠይቋል


ባቡል ኸይር የበጎ አድራጎት ድርጅት፣ በቤተል አለም ባንክ የምገባና የአረጋዊያን መጠለያ ሁለገብ ማዕከል ፕሮጀክት ዋና መሥሪያ ቤትን በ1.2 ቢ.ብር ለማስገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩን ያስታወቀ ሲሆን፤ ለግንባታ ሥራው አቅም ይሆን ዘንድ ከ11 ሚሊዮን በር በላይ ወጪ በማድረግ የከርሰ ምድር የንጹህ ውሃ መጠጥ ማውጣቱንና በ5 ሚሊዮን ብር ወጪ የመብራት ዝርጋታ ማከናወኑን ገለጸ፡፡

በ5ሺ ካሬ ሜትር ላይ መሰረቱ የተጣለውን የባቡል ኸይር የምገባና የአረጋዊያን መጠለያ ሁለገብ ማዕከል ለመገንባት የሁሉም ኢትዮጵያውያን ድጋፍና እገዛ ያስፈልጋል ተብሏል፡፡



በሌላ በኩል፣ የበጎ አድራጎት ድርጅቱ የፊታችን ጥር 4 ቀን 20፞17 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ «አምስት ዓመታትን በሰብአዊነት» በሚል መሪ ቃል የተመሰረተበትን አምስተኛ ዓመት የሚያከብር ሲሆን በዕለቱም በአለም ባንክ አካባቢ መሠረቱ የተጣለለት ይኸው የባቡል ኸይር የምገባና የአረጋዊያን መጠለያ ማዕከል ይጎበኛል ተብሏል፡፡

በዛሬው ዕለት ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት ረፋድ ላይ የባቡል ኸይር በጎ አድራጎት ድርጅት መሥራች ወይዘሮ ሀናን መሀመድና ወጣቱ ባለሃብት ምህረተአብ ሙሉጌታ እንዲሁም ኡስታዝ አብዱር አማሊ ሱልጣን በክብረ በዓሉ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

Addis Admass

04 Jan, 20:22


“ባለስልጣን መሥሪያ ቤቱ የጣለብንን ዕግድ
እንደሚያነሳ ተስፋ አደርጋለሁ”


ከአንድ ሳምንት በፊት በሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን የታገደው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ሃይለማርያም፤ “ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የጣለብንን ዕግድ እንደሚያነሳ ተስፋ አደርጋለሁ” ሲሉ ለአዲስ አድማስ ተናገሩ፡፡ የሚመሩት ማዕከል ከሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ጋር በዕግዱ ዙሪያ እየተመካከረ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ከታገደ አንድ ሳምንቱ መሆኑን የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ አዲስ አበባ የሚገኘው የማዕከሉ ዋና ጽሕፈት ቤት ስራ አቁሞ መዘጋቱን ገልጸዋል። የማዕከሉ የባንክ ሂሳብ መታገዱንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ሕጋዊ መንገድን ተከትሎ ሲንቀሳቀስ መቆየቱን ያስረዱት አቶ ያሬድ፤ ድርጅቱ ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ ባሳለፋቸው አራት ዓመታት ከመንግስት ጫና ደርሶበት እንደማያውቅ አስታውቀዋል። ይሁንና በሌሎች የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ተቋማት ላይ የሚደርሱ ጫናዎችን አስመልክቶ መግለጫዎችን ሲያወጣ መቆየቱን አልሸሸጉም፡፡

በማያያዝም፣ ማዕከሉ ትኩረቱን በጋዜጠኞችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ላይ በማድረግ፣ ከተለያዩ ወገኖች የሚደርስባቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እንደሚያጋልጥ ዋና ዳይሬክተሩ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል።

ታህሳስ 16 ቀን 2017 ዓ.ም. የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ለማዕከሉ ደብዳቤ ከመጻፉ አስቀድሞ ምንም ዓይነት የማስጠንቀቂያም ሆነ የምርመራ ሂደት እንዳልተከናወነ አቶ ያሬድ አስረድተዋል። ይህንን አስመልክቶም ማዕከሉ ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ደብዳቤ እንደጻፈና በዕግዱ ዙሪያ ከመስሪያ ቤቱ ጋር እየመከረ መሆኑን ጠቁመው፤ “ባለስልጣኑ የጣለብንን ዕግድ እንደሚያነሳ ተስፋ አደርጋለሁ” ተናግረዋል።


የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል፣ በሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ዓዋጅ መሰረት በ2013 ዓ.ም. የተመሰረተ ተቋም ነው።

Addis Admass

04 Jan, 20:21


የ25 ዓመት ረዥም ጉዞ የተጀመረው በዚህ ነው!!

ውድ የአዲስ አድማስ ቤተሰቦች፡- የመጀመሪያው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ታትሞ ለንባብ የበቃው ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም ነበር - የዛሬ 25 ዓመት በዕለተ ቅዳሜ፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶ ያለ አንድ ቅዳሜ በስተቀር ጋዜጣው ያልወጣበት ቀን የለም፡፡ እሱም ቢሆን የተከሰተው በ97 ምርጫ ማግስት በተከሰተው ፖለቲካዊ ቀውስ ሳቢያ ነበር፡፡

የዛሬ 20 ዓመት፣ የአዲስ አድማስ ጠንሳሽ፣ መሥራችና ባለቤት አሰፋ ጎሳዬ (አሴ) በድንገተኛ ህመም ህይወቱ ባለፈበት ወቅት እንኳን ጋዜጣው ሳይታተም አልቀረም፡፡ ረቡዕ ከቀብር በኋላ ቢሮ ገብተን የቅዳሜውን ጋዜጣ ስናዘጋጅ ትዝ ይለኛል፡፡ እያነባንም ቢሆን የቅዳሜውን ሳምንታዊ ጋዜጣ በጉጉት ለሚጠብቀን ውድ አንባቢ አድርሰናል፡፡

አሁን ሳስበው ታዲያ ያኔ ትክክለኛ ሥራ ነው የሰራነው፡፡ የአሴ ነፍስ በዚያ ተግባራችን ጮቤ እንደረገጠች አልጠራጠርም፡፡ እርሱ በህይወት ባይኖርም አዲስ አድማስ መታተሟ፣ ህልምና ራዕዩን ማስቀጠያ ብቸኛ መንገድ ነበር፡፡

እነሆ ከዚያም በኋላ ሁለት አሰርት ዓመታትን አስቆጥራ፣ በብዙ ውጣ ውረዶችና ተግዳሮቶች አልፍ እነሆ ለ25ኛ ዓመቷ በቅታለች፡፡ በግሉ ፕሬስ ሩብ ክፍለዘመን ቀላል ጊዜ አይደለም፡፡ ቀላል ዕድሜ አይደለም፡፡ የ25 ዓመት ጉዞ ሀ ብሎ የተጀመረው ግን በዚህ ነው፡፡ ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም በታተመችው አዲስ አድማሰ ጋዜጣ፡፡

እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን!!

Addis Admass

04 Jan, 20:13


አዲስ አድማስ ጋዜጣ 25 ዓመት ሞላው!

የአዲስ አድማስ ጋዜጣ የመጀመሪያው ዕትም ለንባብ የበቃው ታህሳስ 29 ቀን 1992 ዓ.ም ነው፡፡ ጋዜጣው በመጪው ሳምንት ማክሰኞ 25ኛ ዓመት ይሞላዋል፡፡ ይህንንም ምክንያት በማድረግ፣ ቅዳሜ ጥር 3 ቀን 2017 ዓ.ም፣ የ25ኛ ዓመት ልዩ ዕትም ለንባብ ይበቃል፡፡

ጋዜጣው በእርግጥም ልዩ ዕትም ነው፡፡ በተባ ብዕራቸው የሚታወቁ የአገሪቱ አንጋፋ ደራስያንና ጸሃፍት በሳል ጽሁፎቻቸውን ያቀርቡበታል፡፡ የተለያዩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ጥበባዊ ርዕሰ ጉዳዮች ይዳሰሳሉ፡፡ ከአዲስ አድማስ ጋር የተያያዙ ማራኪ ትዝታዎችና ገጠመኞች ይነበቡበታል፡፡ ባለፉት 25 ዓመታት በአዲስ አድማስ ላይ ከወጡ ጽሁፎች የተመረጡ በዚህ ልዩ ዕትም ይካተታሉ፡፡

እርስዎም ድርጅትዎንና ምርትዎን በዚህ የ25ኛ ዓመት ልዩ ዕትም ጋዜጣ ላይ በማስተዋወቅ የአዲስ አድማስ አጋር ይሆኑ ዘንድ በአክብሮት ተጋብዘዋል፡፡ የልዩ ዕትም የማስታወቂያ ዋጋ ዝርዝርን ከዚህ ደብዳቤ አጋር አያይዘን ልከናል፡፡

ስለ አጋርነትዎ ከወዲሁ እናመሰግናለን

Addis Admass

03 Jan, 07:16


ወርቅ ለማውጣት ሲባል ያልተፈቀዱ ኬሚካሎችን የሚጠቀሙ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ቢሮው አሳሰበ
በትግራይ ክልል ወርቅ ለማውጣት ሲባል ያልተፈቀዱና ማህበረሰቡ ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ኬሚካሎችን የሚጠቀሙ አካላት ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ የክልሉ የመሬትና ማዕድን ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ፍስሃ ግርማይ ለኢፕድ እንደገለጹት፤በክልሉ የነበረው ጦርነት የማዕድን ዘርፉ ላይ ህገወጥ ተግባር እንዲስፋፋ አድርጓል።
በዚህም ህገወጥ ማዕድን አውጪዎች ወርቅ ለማውጣት ያልተፈቀዱና ማህበረሰቡ ላይ ጉዳት የሚያስከትሉ ኬሚካሎች ሲጠቀሙ ቆይተዋል።
ይህም በክልሉ ወንዝ፣ የእንስሳት ሃብት እና በማህበረሰቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሱንና እያደረሰ መሆኑን ተናግረው፤ በክልሉ በህገወጥ መንገድ የማዕድን ንግድ ላይ የሚሳተፉ እና ማህበረሰቡ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ኬሚካሎችን የሚጠቀሙ የማዕድን አውጪዎች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሳስበዋል።
ይህንን ለመፍታት የቁጥጥር መመሪያ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ያሉት አቶ ፍስሃ፤ ከዚያም ተጠያቂነትን የማስፈን እና ህገወጥ ማዕድን አውጪዎችን ለህግ የማቅረብ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።
በቀጣይ ደግሞ ለማዕድን አውጪዎች የሚሰጠው ፈቃድ ይቆማል ብለዋል።
በማዕድን ዘርፉ ህጋዊ ያልሆኑትን ወደ ህጋዊ ሥርዓት የማስገባት ሥራ እየተሰራ ሲሆን በዚህም በ30 ማህበራት የታቀፉ ወጣቶች በህጋዊ መንገድ እንዲንቀሳቀሱ ተደርጓል።
ለነዚህም ህጋዊ ፍቃድ፣ የመሥሪያ ቦታና ሌሎች ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ሥራ ገብተዋል ብለዋል።
ይህ እንቅስቃሴ በክልሉ የማዕድን ሀብት ላይ ሲታይ የነበረውን ህገወጥ ተግባር እንዲቀንስ እና ወደ ብሔራዊ ባንክ የሚገባው የወርቅ ክምችት እንዲጨምር አድርጓል ብለዋል።
(ኢፕድ)

Addis Admass

03 Jan, 07:04


በካሊፎርኒያ አውሮፕላን ተከስክሶ የሁለት ሰዎች ሕይዎት አለፈ

በካሊፎርኒያ ፉለርተን ከተማ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ የሁለት ሰዎች ሕይዎት ማለፉ ተሰምቷል፡፡

አደጋውን ተከትሎ የፉለርተን ከተማ ፖሊስ በሰጠው ማብራሪያ÷ ከሞቱት በተጨማሪ በ18 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን አስታውቋል፡፡

የአደጋው መንስዔም እየተጣራ ነው መባሉን ጠቅሶ ስፑትኒክ ዘግቧል፡፡

Addis Admass

02 Jan, 21:10


ብሪክስ 9 ሀገራትን በአጋርነት ተቀበለ

*
ብሪክስ 9 ሀገራትን በአጋርነት መቀበሉ ታውቋል፡፡

ጥምረቱ በአጋርነት የተቀበላቸው ሀገራትም ቤላሩስ፣ ቦሊቪያ፣ ኩባ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ካዛኪስታን፣ ማሌዥያ፣ ታይላንድ፣ ኡጋንዳ እና ኡዝቤኪስታን ናቸው፡፡

እ.አ.አ በጥቅምት ወር 2024 በሩሲያ ካዛን በተካሄደው የብሪክስ ጉባኤ ላይ 13 ሀገራት ጥምረቱን በአጋርነት እንዲቀላቀሉ ግብዣ ቀርቦላቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡

በሩሲያ፣ ቻይና፣ ህንድ እና ብራዚል የተመሰረተው ብሪክስ ፤ ደቡብ አፍሪካን እ.አ.አ በ2010 ፤ ኢትዮጵያን፣ ኢራንን፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን እና ግብጽን ደግሞ እ.አ.አ በ2024 በአባልነት መቀበሉ ይታወቃል፡፡

እንደ ቻይና እና ሩሲያ ያሉ የዓለም ኃያላን ሀገራትን ያቀፈው ብሪክስ ከ3.5 ቢሊዮን የሚበልጥ ሕዝብን እንደሚወክል ዘ ሳውዝ አፍሪካን ዶት ኮም ዘግቧል፡፡

Addis Admass

02 Jan, 20:43


የተሽከርካሪዎችን ታርጋ መፍታትና መንጃ ፈቃድን መንጠቅ የሚያስቀረው ቴክኖሎጂው፤ አሽከርካሪዎች ቅጣት ለመክፈልም ሆነ ታርጋና መንጃ ፈቃድ ለማስመለስ የሚያባክኑትን ጊዜ ይታደጋል፡፡

የኢንፍራ ቴክኖሎጂ መሥራችና ባለቤት ኢንጂነር ቀዳማዊ ሙሉአለም፤ የትራፊክ ቅጣትንና የፓርኪንግ ክፍያን የሚያዘምነውን ሶፍትዌር ለማበልጸግ አንድ ዓመት ገደማ እንደወሰደባቸው ተናግረዋል፡፡

በከተማዋ በዓመት ከ2.2 ሚሊዮን በላይ የደንብ መተላለፎች እንደሚከሰቱ የተጠቆመ ሲሆን፤ 52 በመቶ የሚሆኑት ተሽከርካሪዎች ከፍጥነት በላይ እንደሚያሽከረክሩ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ የበርካቶችን ህይወት የሚቀጥፈውና ንብረት የሚያወድመው የትራፊክ አደጋ መንስኤው በአብዛኛው የደንብ መተላለፍ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በትራፊክ አደጋ ሳቢያም በዓመት ከ300 – 400 የሚደርሱ ሰዎች ህይወታቸውን ያጣሉ፡፡


አዲስ የበለጸገው ቴክኖሎጂ የትራፊክ ቁጥጥርን በማሳለጥና የመንገድ ደህንነትን በማረጋገጥ፣ በትራፊክ አደጋ የሚደርሰውን ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንደሚቀንስም ነው የተገለጸው፡፡ ቴክኖሎጂው በተጨማሪም የትራፊክ ፖሊሶች የተሰረቁ መኪኖችን በቀላሉ መለየትና ማወቅ ያስችላቸዋል ተብሏል፡፡

የትራፊክ ማኔጅመንት ሥርዓት ከማኑዋል ወደ ዲጂታል መቀየሩን ተከትሎ የትራፊክ ፖሊሶች የታብሌት ተጠቃሚ እንደሚሆኑ የገለጹት የኢንፍራ ቴክ መሥራች ኢንጂነር ቀዳማዊ፤ ለ1500 የትራፊክ ፖሊሶች ታብሌቶችን ወደ አገር ውስጥ ማስገባታቸውን ተናግረዋል፡፡

ለመዲናዋ የትራንስፖርት እንቅስቃሴና ፍሰት መሻሻል ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ የተነገረለት ቴክኖሎጂው፤ ለከተማዋ የትራንስፖርት ዘርፍ ትልቅ ስኬትና የምሥራች ነው ተብሏል፡፡

Addis Admass

02 Jan, 20:41


የከተማዋን የትራፊክ ቁጥጥር የሚያዘምን ቴክኖሎጂ ይፋ ሆነ

• የተሽከርካሪዎችን ታርጋ መፍታትና መንጃ ፈቃድ መንጠቅን ያስቀራል

• የትራፊክ ቅጣትን ከቤት በቴሌ ብርና በሲብር መክፈል ያስችላል

• የተሰረቁ ተሽከርካሪዎችን በቀላሉ መለየትና ማግኘት ይቻላል


የአዲስ አበባን የትራፊክ ቁጥጥርና የፓርኪንግ ክፍያን የሚያዘምን አዲስ ቴክኖሎጂ ይፋ ተደረገ፡፡ የአዲስ አበባ ትራፊክ አስተዳደር ባለሥልጣን፣ ዛሬ ጠዋት በሸራተን አዲስ በተካሄደው መርሃግብር፣ የቴክኖሎጂውን በይፋ ሥራ መጀመር አብስሯል፡፡


ኢንፍራ ቴክ በተባለው የቴክኖሎጂ ኩባንያ የበለጸገው ሶፍትዌር፣ የትራፊክ ቅጣትንና የፓርኪንግ ክፍያን እንደሚያዘምን የተገለጸ ሲሆን፤የከተማዋን የትራፊክ አስተዳደር ሥርዓት ከማኑዋል አላቅቆ ሙሉ በሙሉ ዲጂታላይዝ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል፡፡


አዲሱ ቴክኖሎጂ ለትራፊክ ቅጣት ፓድ ህትመት ብቻ በዓመት የሚወጣውን ከ7 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያስቀር የተነገረ ሲሆን፤ የትራፊክ ቅጣትን ከቤት ተቀምጦ በቴሌብርና በሲብር መክፈል የሚያስችል ነው፡፡

አሽከርካሪው በ8 ባንክ አማራጮች ቅጣቱን መክፈል ይችላል ተብሏል፡፡

Addis Admass

02 Jan, 20:17


10ኛው ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት በጅማ ተመረቀ
ሆቴሉ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጥቶበታል
የሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማሮ 15ኛ ዓመቱን እያከበረ ነው

Addis Admass

02 Jan, 14:52


ሐይሌ በሐይሌ ግራንድ አዲስ አበባ ሆቴል እና በሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት ወላይታ ለምርቃት ሊወጣ የነበረውን 4 ሚሊዮን ብር ለየአካባቢው ት/ቤቶችና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች መሰጠቱም ተብራርቷል።
የዛሬ 15 ዓመት የሐዋሳው ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት እንዲገነባ መሬት በመፍቀድ ከ24 ዓመት በፊት አስተዋፅኦ ያደረጉት የቀድሞው የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የነበሩት አቶ አባተ ኪሾ በክብር እንግድነት በምርቃቱ ላይ ተገኝተዋል።

Addis Admass

02 Jan, 14:52


በይቻላል መርሁ የሚታወቀው አትሌት ሻለቃ ሐይሌ ገብረ ስላሴ የወላይታውን ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት ባስመረቀ በ10ኛ ወሩ የጅማውን የጅማውን ማስመረቁ የተገለፀ ሲሆን ይህም በአንድ ዓመት ከአምስት ወር አንድ ሆቴል ለመገንባት የገባነውን ቃል ማክበራችንን ያሳያል ብሏል አትሌት ሐይሌ ገብረ ስላሴ።
የጅማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ቲጃኒ ናስር በምርቃቱ ላይ ባደረጉት ንግግር ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ ጅማ የበለጠ እንድትፈለግና የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን ሻለቃ ሐይሌ ትልቅ ስራ ሰርቶልናል እኛም በሕይወት እስካለን የጅማን ሰላም እንጠብቃለን ካሉ በሗላ በሆቴሉ ግንባታ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል።
የጅማ ከተማ ከንቲባ አቶ ጠሐ ቀመር ባደረጉት ንግግር ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት በጅማ ከተማ መገንባቱ ለከተማዋ መስህብነት የጎላ ሚና ከመስጠቱም ባሻገር ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል መፍጠሩና በኢኮኖሚው ላይ የሚያሳርፈው መልካም ተፅእኖ እጅግ የሚያኮራ መሆኑን ተናግረዋል። ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርትጅማ በአሁኑ ጊዜ ለ210 ቋሚ ሰራተኞች የስራ እድል የፈጠረ ሲሆን በሙሉ አቅሙ ስራ ሲጀምር የሰራተኞቹን ቁጥር ወደ 400 እንደሚያሳድግ ማኔጂንግ ዳይሬክተሩ አቶ ጋዲሳ ግርማ ጨምረው ገልጸዋል።
ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት በቀጣይ የሻሸመኔውን እና የደብረብርሃን ከተማ መዳረሻውን በቅርቡ ለማስመረቅና ስራ ለማስጀመር ቀን ከሌት እየሰራ መሆኑን የሐይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች ግሩፕ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ጋዲሳ ግርማ ተናግረዋል።
ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት ቀጣይ መዳረሻውን ወደምስራቅ ኢትዮጵያ በማዞር በድሬደዋና በሐረር አድርጎ በዚያው ወደጎረቤት አገር የመሻገር እቅድ እንዳለውም ተብራርቷል።

Addis Admass

02 Jan, 14:51


10ኛው ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት በጅማ ተመረቀ
ሆቴሉ 1 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር ወጥቶበታል
የሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማሮ 15ኛ ዓመቱን እያከበረ ነው
ለሃይሌ ሆቴሎችና ሪዞርቶች አስረኛ የሆነው ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማ ዛሬ ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓም በጅማ እየተመረቀ ነው። የባለ 4 ኮከብ ደረጃ ያለው ሐይሌ ሆቴልና ሪዞርት ጅማ የተለተያዩ ዘመናዊ አገልግሎቶች የተሟሉላቸው 105 የመኝታ ክፍሎች፣ ሁለት የቪአይፒ አገልግሎት የሚሰጡና እያንዳንዳቸው አራት ክፍል ያላቸው ሁለት ቪላዎች ፣5 የኦዲዮጰቪዢዋል መሳሪያዎች የተሟሉላቸው የስብሰባ አዳራሾች፣ አራት ባህላዊና ዘመናዊ ምግቦችን የሚያቀርቡ ሬስቶራንቶች፣ለመዝናናትም ሆነ ጤንነትን ለመጠበቅ የሚያስችሁ የአዋቂና የህፃናት የመዋኛ ገንዳዎች፣ ጂምናዚየም፣ የስፓ የስቲም ባዝ፣ የሳውና ባዝ ሞሮኮ ባዝ የልጆች መጫዎቻ ቦታና ሌሎች የውበት ማዕከላት ተሟልተውለት ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ባለ አራት ኮከብ ሆቴልና ሪዞርት ስለመሆኑ በምርቃቱ ላይ ተገልጿል።

Addis Admass

24 Dec, 08:18


ምን ዓይነት እናት ነሽ?
አንዱ ልጅሽ ሲያለቅስ፣
አባብለው ብለሽ፣
ከሌላው (ከሌለው) ቀምተሽ፣
እንባውን እያበሽ፣
አይዞህ ብለሽ ሰጥተሽ።
ደግሞ ሌላው ልጅሽ፣
ተበደልኩኝ ብሎ ሲመጣ ወደ አንቺ፣
ሌላውን በድለሽ ችግር የምትፈቺ፣
በ”ተበዳይ” እና በ”በዳይ” አዙሪት፣
እየተሽከረከርሽ የማትሄጂ ወደፊት፣
ምን አይነት እናት ነሽ?
(ነሐሴ 26 ቀን 2012 ዓ.ም፤ዮናስ ታረቀኝ)

Addis Admass

24 Dec, 08:06


በቅፅበት ከፍተኛ ደረጃ እደርሳለሁ አትበል፡፡
ከትምህርት ቤት አንደወጣህ ወዲያው ሃብታም፣ ባለስልጣን፣ ወይም ስኬታማ እሆናለሁ ብለህ አትጠብቅ፡፡ ከፍተኛ ትምህርት ቢኖርህ እንኳ ስኬታማ ለመሆን ብዙ ልምድ ያስፈልግሃል፡፡

Addis Admass

23 Dec, 12:11


“ሰው ነህ የሚል ማተም”

አዳም አባታችን አንደተፈጠረ ገነት ነው
የኖረው
ገነት ለመኖሩ ምክንያት የሆነው
ከፍጥረታት ሁሉ
እጅግ “የከበረ” ሰው ስለሆነ ነው።
እየሱስ በሞቱ
ፍቅሩን የገለፀው
ኤጄቶ ላውራልህ
ፋኖ ሆይ ልንገርህ
ቄሮዬ ሆይ ስማኝ
ሰዎች ለተባልነው ለኔና ላንተ ነው።
የእስልምናም ትምሀርት ተግባራቱ
ሲታይ ከነአበቃቀሉ
ሰውን ያስቀድማል ከፍጥረታት ሁሉ
ስለዚህ አዳምጠኝ
በየትም የሰፈርክ የትም የምትገኝ
አንተ ባለ መውዜር ፥ጎበዙ ቀስተኛ
፥አነተ ባለ ሜጫ
ሰው መሆንን ትተህ
ሁኔታን ሳትመጥን ሳታይ አቻችለህ
ብሄርን አካብደህ
መደብክን አንግሠህ
ጶታህን አስልቀህ
ሐይማኖትን ይዘህ
ከወገንህ ጋራ የገባህ ፍጥጫ
ብሔርን አጉልተህ ትግራዋይ ነኝ ብትል
“ነፃነት “ ገድቦ ብቻ ያስቀርሐል
ቋንቋን አስቀድመህ ኦሮሞ ነኝ
ብትል
ሌላን አስኮርፎ “ወንድም “ያሳጥሐል
በዚህም በዚያም በኩል አማራ ነኝ
ብትል
ስግብግብ አድርጎ “ክብር” ያስርብሐል
ይህ አልበቃ ብሎህ
ጠባብነት ጠልፎህ
ሰው ከሚለው ንግር ሰው ከሚለው
በላይ
የቀለም ደረጃ
የሐብት ደረጃ
የውበት ደረጃ
ምንትስ ደረጃ
እያልክ በመደርደር ዘርዝረህ ብታሳይ
እኔ አልቀበልም ከቁብም አልቆጥረው
ምክንያት ብትለኝ
እግዚያብሔር የሰጠኝ ደረጃዬ ሰው ነው
ፍጥረቴም ከገነት ፍቅሬም ከየሱስ ነው
እናም ኮሚሣሬ ወረዳ መሪዬ
ብሔሬን ሰርዘህ ከመታወቂያዬ
ምኔም ምናምኔም ሰው እንዲመስልልኝ
ክብር እንዲሰማኝ
ነፃነት እንዳገኝ
ወደ ጎጃም ሄጄ ለማለት “ቄሮ “ ነኝ
አሪሲ ተጉዤ ለማለት” ሄጎ” ነኝ
ሲዳማ ዘልቄ ለማለት “ፋኖ” ነኝ
በመታወቂያዬ “ሰው ነህ “
የሚል ማተብ አሳትመህ ስጠኝ።
ሞገስ ተከተል

Addis Admass

23 Dec, 09:24


ዛሬ ማለዳ 38ኛውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤን ከፍ ባለ ሁኔታ ለማስተናገድ የመዲናችንን ቅድመ ዝግጅት ገምግመናል።
የአፍሪካዊያንና የዓለም የዲፕሎማሲ ማዕከል፤ የህብረብሄዊነት አርማ የሆነችዉ ከተማችን አዲስ አበባ ይህንን ታሪካዊ ጉባኤ በደመቀ እና ባማረ መልኩ ለማስተናገድ ከወትሮ በተሻለ መልኩ እንግዶቿን ለመቀበል አስፈላጊውን ቅደመ ዝግጅት በማድረግ ላይ ናት።
የከተማችን ነዋሪዎችም እንግዶችን በተለመደው ኢትዮጵያዊ ጨዋነት እና እንገዳ ተቀባይነት ለመቀበል፣ በየአካባቢዉ ከወዲሁ ከተማችንን ውብ እና ፅዱ በማድረግ እንዲሁም በእንኳን ደህና መጣችሁልን መንፈስ ሃላፊነታችንን በመወጣት የሃገራችንን ስም እና ክብር ከፍ ለማድረግ ተባብረን እንስራ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Addis Admass

23 Dec, 05:41


አዋዋልህን እና ጓደኞችህን ምረጥ፡፡
አስተሳሰብህን እና ድርጊትህን በገንቢ ጎን ከሚተቹና ከሚገነቡ ሰዎች ጋር የምታደርግ ከሆነ በየጊዜው እየተሻሻልክ የምትሄድ ሰው ትሆናለህ፡፡ ባህሪህ እና ህይወትህ እያደር የሚመስለው የጓደኞችህን ነው፡፡

Addis Admass

22 Dec, 16:07


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሱዳን አቻው ተሸነፈ

በአፍሪካ ሀገራት ዋንጫ ውድድር (ቻን) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሱዳን አቻው 2ለ 0 ተሸንፏል፡፡

የሁለቱ ቡድኖች የቻን የመጨረሻ ዙር ማጣሪያ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 11 ሰዓት በሊቢያ ቤንጋዚ ቤኒና ማርትየርስ ስታዲየም ተደርጓል፡፡

በጨዋታውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሱዳን አቻው 2 ለ 0 ተሸንፏል፡፡ (ኤፍ ኤም ሲ)

Addis Admass

22 Dec, 10:14


አትሌት ስለሺ ስህን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ሆኖ ተመረጠ

Addis Admass

22 Dec, 09:53


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በታደሰው እና የቅርስ ሀብቱ ለእይታ በቀረበበት ብሔራዊ ቤተመንግሥት የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮንን ተቀብለዋል።

Addis Admass

21 Dec, 19:57


የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በዓድዋ ድል መታሰቢያ ሐውልት ስር የአበባ ጉንጉን አስቀመጡ

የፈረንሳይ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የጥቁር ሕዝቦች ኩራት በሆነው የዓድዋ ድል መታሰቢያ በመገኘት ለጥቁር ሕዝቦች ነፃነት ትግል መሥዋዕት ለከፈሉ ጀግኞች መታሰቢያ ሐውልት ሥር የአበባ ጉንጉን ማስቀመጣቸውን ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ።

ከንቲባዋ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ፕሬዚዳንቱ የዓድዋ ድል መታሰቢያን መጎብኘታቸውንም ገልጸዋ።

ፕሬዚዳንት ማክሮን በዚሁ ወቅት አዲስ አበባ ባሳየችው ፈጣን ለውጥ መደነቃቸውን ገልጸዋል።

ከንቲባ አዳነችም በራሳቸው እና በከተማ አስተዳደሩ ለፕሬዚዳንቱ ስም ምስጋናቸውን አቀርብዋል።

Addis Admass

21 Dec, 19:49


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያዩ
**

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው “ከፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር በብሔራዊ ቤተመንግሥት በነበረን የሁለትዮሽ ውይይት ሰፋ ያለ መጠነርዕይ ባላቸው የሁለትዮሽ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገናል” ብለዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ እና የፈረንሳይ መንግሥት በብሔራዊ ቤተመንግስት እና በመካሄድ ላይ ባለው የላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት እድሳት ሥራዎች ላይ ላደረጉት አስተዋፅዖም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ “በውይይታችን በተለያዩ ዘርፎች የሚኖሩ ትብብሮችን የፈተሽን ሲሆን የፈረንሳይን ኢንቨስትመንት መጨመርን አስመልክቶ ብሎም በትምህርት እና ባሕል ዘርፎች ያለንን ግንኙነት በማጠናከር ጉዳዮች ላይ ተነጋግረናል” ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በውይይቱ የሀገራቱን ታሪካዊ ትስስር ይበልጥ የመገንባት አስፈላጊነት ላይ አፅንዖት መስጠታቸውንም አመላክተዋል፡፡

Addis Admass

21 Dec, 19:35


የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገቡ

Addis Admass

07 Dec, 19:56


ወጣቱ ባለሃብት ከ2 ሚ. ብር በላይ ድጋፍ አደረገ


• ባቡል ኬይር በቀን ከ4 ሺ በላይ ወገኖችን ይመግባል



በተለያዩ የበጎ አድራጎትሥራዎች ላይ ገንዘቡንና ጊዜውን በመሥጠት በንቃት የሚሳተፈው ወጣቱ ባለጸጋ ምህረትአብ ሙሉጌታ፤ በዛሬው ዕለት አበበ በቂላ ስቴዲየም አካባቢ ባለው ባቡልኬይር በመገኘት ከ1 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ የ4ሺ ሰው የምሳ ወጪ ሸፍኗል፡፡

ከዚህም ባሻገር፣ ድርጅቱ እየሰራ ያለውን የበጎ አድራጎት ለማገዝ የ1 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል።

ስጦታውን የተረከቡት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ሀናን ማህሙድ ምህረት አብ፣"ዛሬ ሰርፕራይዝ ነው ያደረግኸን፤ ይሄን ያህል መጠን ያለው ድጋፍ ሲደረግልን የመጀመሪያው ነው።" ሲሉ ለባለሃብቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በሀገራችን በራስ ተነሳሽነት በደጋግ ኢትዮጵያውያኖች ከተመሠረቱ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች መካከል ባቡል ኬይር የበጎ አድራጎት ድርጅት አንዱ ሲሆን፤ድርጅቱ ከተመሠረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ አስታዋሽ ያጡ ኢትዮጵያውያንን በመርዳት ላይ ይገኛሉ፡፡ ባቡል ኬይር በቀን ከ4 ሺ በላይ ወገኖችን ይመግባል፡፡

Addis Admass

07 Dec, 12:00


በአማራ ክልል  በአንድ ቀን ብቻ 5 ባንኮች ተዘረፉ

በአማራ ክልል በዚህ ሳምንት በአንድ ቀን ብቻ አምስት ባንኮች በታጠቁ ሃይሎች  መዘረፋቸው ተነገረ፡፡ ባንኮቹ  የተዘረፉት በሰሜን ወሎ ዞን፣ ሲሪንቃ ከተማ ነው፡፡

በታጣቂ ሃይሎች ተዘረፉ የተባሉት የአቢሲኒያ ባንክ፣ አባይ ባንክ፣ ፀደይ ባንክ፣ ንግድ ባንክና  ቡና ባንክ ቅርንጫፍ ባንኮች  ናቸው፡፡

የባንኮቹ አመራሮች  ዘረፋውን በተመለከተ እስካሁን የሰጡት   ዝርዝር መረጃ ወይም መግለጫ የለም፡፡
 


በክልሉ በመንግሥት ሃይሎችና ታጣቂ ቡድኖች መካከል ውጊያ ከተጀመረ ከአንድ ዓመት  ወዲህ፣  የጸጥታና ደህንነት ሁኔታው እያሽቆለቆለ መምጣቱ ይታወቃል፡፡

Addis Admass

07 Dec, 11:25


ጋናውያን  ዛሬ ፕሬዚዳንታቸውን እየመረጡ ነው

•  ሳህለወርቅ ዘውዴ የኃብረቱን የምርጫ ታዛቢ ቡድን ይመራሉ


የምዕራብ አፍሪካዊቷ  አገር ጋና  በዛሬው ዕለት ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እያካሄደች ሲሆን፤ የአፍሪካ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድኑን  እንዲመሩ  የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ ተሰይመዋል፡፡ ሳህለወርቅ ዘውዴ  ከፕሬዚዳንትነት ሥልጣናቸው መሰናበታቸውን ተከትሎ፣ ለአህጉራዊ  ከፍተኛ ሃላፊነት ሲሰማሩ  ያሁኑ  የመጀመሪያቸው ነው፡፡

ላለፉት አስርት ዓመታት  በአስከፊ የኢኮኖሚ ቀውስ ውስጥ እየተንገዳገደች የዘለቀችው  ጋና፤ በስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዚዳንት የስልጣን ዘመን መጠናቀቁን ተከትሎ ነው ዛሬ ምርጫ የምታካሂደው፡፡

በምርጫው ገዥው አዲሱ የአርበኞች ፓርቲና የተቃዋሚው ብሔራዊ  ዴሞክራቲክ ኮንግረስ የተባሉት አውራ ፓርቲዎች በግንባር ቀደምትነት እየተፎካከሩ እንደሚገኙ ተዘግቧል፡፡

Addis Admass

06 Dec, 21:04


ውድ አንባቢያን

ሳምንታዊ የቅዳሜ ጋዜጣችሁን አዲስ አድማስን፣ በእነዚህ
የመዲናችን መፃሕፍት መደብሮች ውስጥ እንደምታገኙት
ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
• ጃፋር መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ)
• ክብሩ መፃሕፍት መደብር (ጥቁር አንበሳ፣ ትራኮን ህንጻ)
• እነሆ መፃሕፍት መደብር (አራት ኪሎ)
• ኢዞጵ መፃሕፍት መደብር (አቡነ ጴጥሮስ)
• አምደ መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ) አዲስ አድማስ የእርስዎና ቤተሰብዎ

Addis Admass

06 Dec, 21:02


በመቐለ ማንኛውም ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይካሄድ ተከለከለ


በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት በመቐለ ከተማ ተደረግብኝ ላለው የከንቲባ መፈንቅለ ስልጣን "ሰላማዊ ስልፍ እንዳካሂድ ይፈቀድልኝ " ሲል በመቐለ የህወሓት ፅህፈት ቤት በኩል ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ ጥያቄ አቅርቧል።

ቡድኑ ሰልፉን እሁድ ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 እስከ ቀኑ 6:30 ለማድረግ ነበር የጠየቀው።

ቡድኑ ደብዳቤው ፤ "ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም የተፈፀመው በመሳሪያ የተደገፈ የመቐለ ከተማ መደበኛ አስተዳደር መፈንቅለ ስልጣን ለማውገዝ" ነው ብሏል። በተጨማሪም ፥ " ለዘመናት በከፈልነው መስዋእት ያፀናነው መብታችንና የመሰረትነው ምክር ቤት በአዲስ ገዢ ግለሰቦች አምባገነንነት ሲፈርስ አንታገስም" ሲል ገልጿል።

ለመቐለ ህወሓት ፅህፈት ቤት ደብዳቤ ዛሬ አርብ ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም ምላሽ የሰጠው የመቐለ ከተማ አስተዳደር በበኩሉ፤ የከተማው ጥምር ኮሚቴ በሰጠው መምሪያ መሰረት በመቐለ ከተማ ማንኛውም ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይካሄድ ተከልክሏል ብሏል።

Addis Admass

06 Dec, 20:28


https://t.ly/MXShA

Addis Admass

06 Dec, 20:27


https://t.ly/XO8-H

Addis Admass

06 Dec, 19:46


የኢትዮ-ቻይና የቲቪና ፊልም ፌስቲቫል ሊካሄድ ነው


የኢትዮጵያና ቻይና የባህል ቁርኝትን ለማጠናከር ያለመና የብሪክስ አገራት የቲቪና የፊልም ፌስቲቫል ማስጀመሪያ የሆነው የኢትዮ- ቻይና የቲቪና ፊልም ፌስቲቫል ሊካሄድ እንደሆነ ተገለጸ፡፡


ዛሬ ህዳር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. በቶንግዳ ሆቴል ለጋዜጠኞች በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተነገረው፤ ከታህሳስ 11 እስከ 14 ቀን 2017 ዓ.ም፣. በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ራስ መኮንን አዳራሽ የሚካሄደው ፌስቲቫል ዋነኛ ዓላማው፣ በኢትዮጵያና በቻይና ለሚገኙ የፊልም ተቋማት የልምድና የዕውቀት ሽግግር ለማድረግና በሁለቱ አገራት መካከል የባሕል ቁርኝቱን ለማጠናከር ነው ተብሏል፡፡


ፌስቲቫሉ ከኢትዮጵያ ባሻገር ለመላው የአፍሪካ አገራት የፊልም ኢንዱስትሪ መነቃቃት ትልቅ ዕድል እንደሚፈጠርም ነው የተነገረው፡፡

በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ የባሕል ሃላፊ ዣንግ ውይ፤ ኢትዮጵያና ቻይና የቆየ ግንኙነት ያላቸው አገራት መሆናቸውን ጠቁመው፣ ፌስቲቫሉ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ያጠናክረዋል ብለዋል፡፡ በተጨማሪም፣ ቻይና ለሁለቱ አገራት የባህል ቁርኝት መጠናከር የምታደርገውን ዘርፈ ብዙ ድጋፍ አጠናክራ እንድትቀጥል ትልቅ እድል አንደሚፈጥርላት አስረድተዋል።

“ቻይና ለፊልም ኢንዱስትሪው የምታደርገውን የቁሳቁስ ድጋፍ አሁንም አጠናክራ ትቀጥላለች” ብለዋል፤ ዣንግ ውይ።

Addis Admass

06 Dec, 19:46


የኢትዮጵያ የባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ወይዘሮ ነፊሳ አልማሕዲ በበኩላቸው፤ ረዥም ልምድና ዕውቀት ካላቸው የቻይና የፊልም ባለሞያዎች ጋር ይህን የመሰለ ግንኙነት መፍጠር ትልቅ ዕድል ነው ብለዋል። አክለውም፤ “ኢትዮጵያም ያሏትን የፈጠራ ኢንዱስትሪዎች የበለጠ ለማጠናከር ፌስቲቫሉ አስፈላጊ ነው” ብለዋል።


የመጀመሪያው የብሪክስ የፊልም ፌስቲቫል ማስጀመሪያ የሆነው የኢትዮ ቻይና የፊልምና ቲቪ ፌስቲቫልን፣ የጎፍ ኢንተርቴይመንት ከባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር እንዲሁም ከቻይና ኤምባሲ ጋር በመሆን እንደሚያዘጋጁት ለማወቅ ተችሏል፡፡

Addis Admass

06 Dec, 08:56


“በፌዴሬሽን ስለመመረጤ የማውቀው ነገር የለም”

የአዲስ አበባ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን በትላንትናው ዕለት በጊዮን ሆቴል ዓመታዊ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሄደ ሲሆን፤ ለቀጣይ  አራት ዓመታት የሚመሩትን ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንትና የሥራ አስፈጻሚዎች መርጧል፡፡

ፌዴሬሽኑ  ሁለት ታዋቂ ሴት  አርቲስቶችን በአመራርነት ማካተቱም ይታወቃል፡፡

በሥራ አስፈጻሚ ውስጥ ከተካተቱት አንዷ ታዋቂዋ አርቲስት ሐረገወይን አሰፋ ስትሆን፤ እርሷ ግን በሥራ አስፈጻሚነት ስለመመረጧ የምታውቀው ነገር እንደሌለ ገልጻለች፡፡

“እስከ እኩለ ለሊት ድረስ የቆየ ቀረፃ ጨርሼ ስልክ ስከፍት፣ በርካታ ወዳጆቼ ተመረጥሽ የሚል ነገር ሰምተን ነው የሚል መልእክት ልከዋል።“ ያለችው አርቲስቷ፤ ”በወዳጆቼ ጥቆማ ወደ ማህበራዊ  ሚዲያ ስገባ ተሰራጭቶ ያየሁት መረጃ  በፍፁም የማላውቀውና ከሌላው ሰው ዘግይቶ የደረሰኝ ነበር” ብላለች፤ በማህበራዊ ትስስር ገጽዋ ባጋራችው ጽሁፍ፡፡

በግሌ በፕሮሞሽን፣ መድረክ በመምራትና መሰል ጉዳዮች በሙያዬ እንዳግዝ በስልክ ተጠይቄ፣ “ፍቃደኛ ነኝ በሙያዬ አግዛችኋለሁ” የሚል  ምላሽ ሰጥቻለሁ ያለችው ሃረገወይን፤ መረጃዎችን  ላኪልን ስባልም በፍቃደኝነት ልኬያለሁ ብላለች፡፡

“ከዚህ ውጭ ግዮን ሆቴል ተካሄደ ስለተባለው ስብሰባ የማውቀው ነገር አልነበረም፤ በቦታውም አልነበርኩም፤ጥሪም አልደረሰኝም።” ብላለች፤ አርቲስት ሃረገወይን አሰፋ፡፡

Addis Admass

05 Dec, 19:21


“ብሔራዊ አጀንዳዎቻችን ላይ አንድ ሆነን መቆም አለብን”


ኢትዮጵያውያን ግጭቶችና ልዩነቶችን ከሚፈጥሩ አጀንዳዎች ይልቅ ብሔራዊ ጥቅምን በሚያስከብሩ አጀንዳዎች ላይ የጋራ አቋም መያዝ እንዳለብን ኡስታዝ ጀማል በሽር ገለጹ፡፡

ኢትዮጵያ የዓባይ ጉዳይን በተመለከተ ያላትን አቋም ለአረብ ሀገራት በአረብኛ ቋንቋ በስፋት በማድረስ የሚታወቁት ኡስታዝ ጀማል በሽር፤ እንደ ሕዝብ ብሔራዊ የሆኑ አጀንዳዎቻችን ላይ አንድ ሆነን መቆም አለብን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኡስታዝ ጀማል ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ጋር ባደረጉት ቆይታ፣ ግብጻውያን በመሀከላቸው መከፋፈል ቢኖርም በሀገር ጉዳይ ላይ ያላቸው አንድነት ጠንካራ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡

“ግብጻውያን በየትኛውም የሥራ ዘርፍ ላይ የሚገኙ ፤ ረጅም ዓመት ተፈርዶባቸው በእስር የሚገኙ ዜጎቻቸው ጭምር በሀገራቸው ጉዳይ ያላቸው አቋም አንድ ከመሆኑም በላይ ጠንካራ ነው፡፡” ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ የዓባይ ውሃ ባለቤት ብትሆንም በዜጎች ዘንድ የሚሰጠው ትኩረት ሊሠራበት የሚገባው መሆኑንም አንስተዋል፡፡ በትምህርት ሥርዓታችን ውስጥ ተተኪ ለሆኑ ትውልዶች ኢትዮጵያ ያላትን የውሃ ሀብትና የዓባይን ውሃ የተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ትኩረት ተሠጥቶ በመሥራት ረገድ ያለን ተሞክሮ ደካማ መሆኑን በመግለጽም፤ ይህ ጉዳይ ሊሻሻል እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡

ኡስታዝ ጀማል ሀገርን ወክለው በዓባይ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያ ያላትን አቋም በማሳወቅ፣ በበርካታ የመገናኛ ብዙሃን ላይ በመቅረብና የራሳቸውንም ሚዲያ በማቋቋም በአረብኛ ቋንቋ በመሞገት ይታወቃሉ፡፡

Addis Admass

05 Dec, 18:45


በመጨረሻም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ክልላዊ ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ያለበትን ሃላፊነት ለመወጣት በሚያስችለው አግባብ ላይም አቅጣጫ በማስቀመጥ ውይይቱ መቋጨቱ ታውቋል፡፡

በሌላ በኩል፤ በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው የህወሓት ቡድን፣ የፊታችን እሁድ ህዳር 29 ቀን 2017 ዓ.ም በመቀሌ ከተማ የተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ፈቃድ መጠየቁ ተሰምቷል፡፡

ቡድኑ ለመቀሌ ከተማ አስተዳደር በጻፈው ደብዳቤ እንደገለጸው፤ “ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም በትጥቅ የተደገፈ የአስተዳደር ፈረሳ በመከናወኑ፣ ይህን ለመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ እናደርጋለን” ብሏል። ለዚህም የከተማ አስተዳደሩ ፈቃድ እንዲሰጠው ቡድኑ ጠይቋል፤ በደብዳቤው፡፡

“ለዘመናት መስዋዕት ከፍለን የመሰረትናቸው ምክር ቤቶች በግለሰቦች ሲፈርሱ አንታገስም በሚል ምክንያት፤ ከህዝባችንና አባላቶቻችን በተደጋጋሚ ጥሪ እየቀረበልን በመሆኑ ህዳር 29 በመቀሌ ከተማ ሰልፍ ለማድረግ አቅደናል” ብሏል፤ ቡድኑ።

እሁድ ህዳር 29 ከጠዋቱ 2 ሰዓት እስከ 6:30 ሰልፉን ለማድረግ ተዘጋጅተናል ያለው የህወሓት ቡድን፤ የጸጥታ ኃይል ጥምር ኮሚቴ ሰልፉን እንዲፈቅድለትና ከለላ እንዲያደርግለት ጠይቋል፤ በመቀሌ የህወሓት ጽ/ቤት፡፡

Addis Admass

05 Dec, 18:45


የትግራይ የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች ጠ/ሚኒስትሩ
በተገኙበት በአዲስ አበባ ውይይት አድርገዋል


• በመቀሌ የህወሓት ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ፈቃድ ጠየቀ


የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳና የህወሓት ሊቀመንበር ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልን ጨምሮ የክልሉ የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች በአዲስ አበባ፣ ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት፣ ከፌደራል መንግሥት አመራሮች ጋር በትግራይ ክልል ባለው አጠቃላይ የፖለቲካ፣ የአስተዳደርና የጸጥታ ሁኔታ ላይ ዛሬ ውይይት ማድረጋቸው ታውቋል፡፡

በውይይቱም ላይ በክልሉ የሚታዩ ችግሮችን እንዴት በጋራ መፍታት እንደሚገባ ምክክር የተደረገ ሲሆን፤ በተለያዩ አንኳር ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ የጋራ አቅጣጫዎች መሠረት በጋራ ለመስራትና የክልሉ ህዝብ የፀጥታ፣ የመልካም አስተዳደርና የልማት ፍላጎት ለማሟላት አስቻይ ሁኔታ ለመፍጠር መግባባት ላይ ተደርሷል ተብሏል።

በተለይም ከመኖርያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቀዬአቸው የሚመለሱበትን ሁኔታ፣ ታጣቂዎች ወደ መደበኛ ሕይወት የመመለስ ሂደትን በትኩረት በሚሰራበትና በሚሳለጥበት ሁኔታ ላይ መግባባት ተደርሷል።

በተጨማሪም በክልሉ ያሉ የተፈጥሮ ሃብቶች አጠቃቀም ህጋዊ በሆነ አግባብ የህዝብንና የሀገርን ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሆን፣ ለህዝብ የሚቀርቡ የመንግስት አገልግሎቶች የሚሻሻሉበትና የህዝብን ፍላጎት የሚመጥኑ እንዲሆኑ፣ ቀጣይነት ያለው ጠንካራ ስራ እንዲሰራ ተገቢው አቅጣጫ በውይይቱ መለየቱ ተነግሯል፡፡

Addis Admass

05 Dec, 17:50


በተጨማሪም በቴክኖሎጂ፣ እውቀት ሽግግርና በኮንስትራክሽን እንዲሁም በቤት አስተዳደር ሥራዎች ዘመናዊ የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል መሆኑም ተነግሯል፡፡

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ረሻድ ከማል፤ ኮርፖሬሽኑ በፕሮጀክት አስተዳደር ረገድ በሞዴልነት የሚጠቀስ ስርዓት መዘርጋት የቻለ ተቋም እንደሆነ ገልጸዋል።

በአሁኑ ሰዓት የኮርፖሬሽኑ የግንባታ ፕሮጀክቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ በመሆኑ የተቋሙን የፕሮጀክትና የሀብት አስተዳደር አቅምን በማሳደግና የአሰራር ሥርዓት በማሻሻል ትርፋማነቱንና ተወዳዳሪነቱን ለማረጋገጥ የሚያስችል ሥራ ከወዲሁ መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ከሎህባወር አሶሴት ኩባንያ ጋር በመሆን ዓለም አቀፋዊ ልምዶችን ተግባራዊ ለማድረግ ኮርፖሬሽኑ እንደሚሰራም አቶ ረሻድ ተናግረዋል፡፡

የሎህባወር አሶሴት ዋና ሥራ አስፈጻሚ በበኩላቸው፤ በከፍተኛ ለውጥ ላይ ካለው ከፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ ለመስራት እድል በማግኘታቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ በዘርፉ ለ28 ዓመታት ያዳበሩትን የማማከር አገልግሎት ልምድ ለኮርፖሬሽኑ ለማከፈል እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

(ዘገባው የኢዜአ ነው)

Addis Admass

02 Dec, 06:17


ትችቱን ረገብ አድርጉት!

በሰማችሁት፣ ባያችሁት እና ባነበባችሁት ነገር ሁሉ ላይ ግምታዊ ሃሳብ ሰጭነት፣ ትችት-ተኮር አስተያየትና አክራሪ አቋም ያዥነት ማንንም ከሚጎዳው በበለጠ ሁኔታ እናንተንው እንደሚጎዳችሁ ታውቃላችሁ?

ከእንደዚህ አይነቱ ልምምድ ጋር ተያይዞ የሚመጣው መዘዝ ብዙ ነው፡፡

በሰው ነገር ጥልቅ እያሉ ከመኖር የሚመጣ ዓላማ-ቢስ ኑሮ መኖር፣ ሌሎችን በማጣጣል ያደግን የመምሰል የውሸት ስሜት እና የመሳሰሉት ተጠቃሽ ናቸው፡፡

የአንድን ነገር የጀርባ ታሪክና አመጣጥ ሙሉ ለሙሉ በማታውቁት ሁኔታ ውስጥ እየገባችሁ ሃሳብ ሰጪነቱን ረገብ አድርጉትና እስቲ ዝም ብላችሁ ራሳችሁን ማሳደግ ላይና ዓላማችሁ ላይ አተኩሩ!

Dr. Eyob Mamo

Addis Admass

01 Dec, 21:09


የወቅቱ ጥቅስ
ያሸነፍን ሲመስለን መሸነፍን እንረሳለን
የተሸነፍን እንደሆነ
ማሸነፍ የኛም አይመስለንም
ሁለቱ መካከል ግን
አንድ አዲስ ልጅ እንወልዳለን፡፡› (የአገሬ ገጣሚ)

Addis Admass

01 Dec, 21:05


አብሰርድ (ወለፈንዴ) ዘመን!

ከሰሞኑ ሽጉጥ ልገዛ ወደ አንዱ ሱቅ ጎራ አልኩ .. በእርግጥ የጦር መሣሪያውን ሳይሆን ለጩጬው የእህቴ ልጅ መጫወቻ ይሆን ዘንድ.. የህፃናቱን ሽጉጥ ነበር የፈለግሁት፤ ውሃ የሚተፋውን ምናምን .. ሆኖም ግን “ children violence “ .. ብለው ከለከሉኝ።
እሱ ደግሞ ምንድነው ብዬ ብጠይቅ .. የልጆች ስነልቦና ተገቢ ባልሆኑ ነገሮች እንዳይመረዝ ከሚደረጉ ጥንቃቄዎች አንዱ እንደሆነና .. ኳስ ብገዛለት ልጁንም እኔንም እንደምጠቅም ነገሩኝ።
ይሄኔ ልጅነቴን አስታውሼ በትካዜ ሰመጥኩ። በእኛ ጊዜ እንኳን መጫወቻዎች የሚያመጡትን ተፅዕኖ ታሳቢ በማድረግ የሚገመግምና የሚጠነቀቅልን አካል ሊኖር ቀርቶ ፤ .. በተረትና በመዝሙር የሚነገሩን ታሪኮች ለአጥፍቶ ጠፊነት የሚያነሳሱ ነበሩ። ለምሳሌ የቢሊጮ ተረት የፖሊስና ህብረተሰብ ዜና ነበር የሚመስለው። የዘመኑ ህፃን ቢሆን ከተዘጋው ዶሴ ዶክመንተሪ ይሰራበት ነበር ..
ቢሊጮ በልጅነቱ እናቱ የሞተችበት ብላቴና ነው .. እንጀራ እናቱ ትበዘብዘዋለች፤ ትበድለዋለች፤ የራሷን ልጆች እንደ እንቁላል እየተንከባከበች ታስቀናዋለች .. ቢሊጮ ነገሮች ከአቅም በላይ ሆነውበት .. ምርር ሲለው ልጇን አርዶ ከትፎ ቀቅሎ፣ እንጀራ እናቱን አታሎ ያበላታል .. ከዚያ የድል መዝሙሩን ይዘምራል ..
“እኔ ቢሊጮ ተበላልጬ
የልጇን ስጋ አበላሁ ልጬ ..” እንዲህ አይነቱን ተረት እየሰማን ፣ ቀለል አድርገን እየዘመርን ነው ያደግነው።
ብዙዎቹ መዝሙሮች ግራ የሚያጋቡ ናቸው። በጥቂቱ ጨለማ የወረራቸው ፣ በታሪካዊ ጀግኖቻችን ላይ እንደመሣለቅ የሚቃጣቸው ፣ ትንቢት ቢጤ የሆኑና አመዛኙ ደግሞ አብዘርድ ( ወለፈንዴነት) የሚስተዋልባቸው፣ አሳዛኝ አንጀት የሚበሉ መዝሙሮች ናቸው። አሁንም “ኩኩ ኩኩዬ .. ኩኩ ኩኩዬ ..”ን ሳስታውስ እንባዬ ይመጣል።
“የአልማዝ ቦርሳ ትልቅ ነው
ቢበረብሩት ባዶ ነው
እሷ ምትሔደው በጋሪ
እኔ ከፍላለሁ ስሙኒ .. “ መሬት ጠብ ያላለ ሀቅ ነው።
ዛሬ አልማዝ ስሟ ኤሚ ሆነ እንጂ ቦርሳዋ ያው ነው .. የጋበዝኳትን እራት ቅርጥፍጥፍ አድርጋ ከበላች በኋላ ጆንያ ሙሉ ስሙኒ አስከፍላኝ ..
“ሳም ሳም አርግና ቶሎ ልቀቀኝ
ቲቸር ይቆጣሉ home work አለብኝን “ ዘምራ እብስ ትላለች።
“አንድ ልጅ ነበረች ጭራሮ ሚሏት
ድንጋይ ላይ ቁጭ ብላ ንፋስ ወሰዳት
የንፋሱ ውሃ ምንጩ ደፈረሰ
ምንም ሳላጠና ፈተና ደረሰ .. ”
የሚለውን “ምንም ላታቀምሰኝ ገንዘቤ ፈሰሰ” ብዬ ለወጥ በማድረግ .. ለጓደኞቼ ሪፖርት እያደረግሁ፣ ይኸው ዛሬም ድረስ እንደተወሰወስኩ አለሁ። መዝሙሮቹ ሁሉ ተስፋ ፣ ድል ፣ ቀና ቀና ነገር የራቃቸው ናቸው ማለት ይቻላል። ለምሳሌ ፤ አወሌ አወል አወሌ .. ሚሊሻ ስልክ ደወሌ
ሚሊሻ የድሮ ጓዴ ፈረሱ ነጭ አረንጓዴ
እንጀራ በጨው እንጀራ በጨው
የአህያን ሹፌር መኪና ገጨው
መኪና መጣ በቁልቁለቱ
ተገለበጠ በጭንቅላቱ ..
ገና ለዓለም እንግዳ በሆነው ለጋ አቅላችን፣ መርዶ ሸምድደን እየዘመርን ነው ያደግነው።
“አለማየሁ ካሳ ጥይቱ 30
አንበሳ ላይ ወጥቶ ሊገለኝ ተነሳ
መኪናው ከርካሳ ተገልብጦ ፈሳ “

ተጨማሪ ያንብቡ
https://t.ly/jyzf2

Addis Admass

01 Dec, 21:00


ኀይለኛው የደርግ አባል! (ጴጥሮስ ገብሬ)

“--በተለይ አርሶ አደር፤ ከባድ ወንጀል ካልፈጸመ በቀር በየትኛውም ሰበብ በፖሊስ ታሥሮ ማደር የለበትም ብለው
ያምናሉ። ይልቅስ ጉዳዩ በአስቸኳይ ታይቶለት ወደ ልማት ሥራው መመለስ አለበት።--”


የታሪክ መለኪያ ዘንጎች ቀናት አይደሉም። የቀናት መልክና ቀለም የሚሠራው፣ጥበቡ የሚያሸበርቀው በሰው ነወና ክብሩ ወይም ውርደቱ የሚያርፈው መልሶ ሰው ላይ ነው።
በየዘመኑ መልካችንን ላጠለሹት፣ውበት ብለን አደባባይ ላይ ላጌጥንባቸው ክብሩንና ውርደቱን ተቀባዩ ሰው ነው። ቅዱስ መጽሐፍ “ቀኑ በትዕዛዝህ ይኖራል”ብሎ ለባለቤቱ የሰጠውን ሥልጣን፣መልሶ ለአዳም ስለሰጠው የተቀበለውን ቀን በደም ነክሮ፣ወይም በልማት አሳምሮ፣በጦርነት በጥብጦ፣ካልሆነም በሰላም ኩሎ ሕይወትን በልጓም አቅጣጫ የሚያስይዛት ሰው ነው። ሰው ደግሞ ክፉም ሆነ ደግ ለማድረግ ከጀርባው ገፊ ምክንያቶች አሉት።
ሒትለር እንደ ዛፍ በቅሎ፣ዝም ብሎ ምድርን አላነደደም።ከጀርባው ሰበብ አለ። እንደየዐውዱ አንዳንዴ ሃይማኖት መድኀኒት ይሆናል። ለጥፋት ደግሞ አስተዳደግ፣ጭቆናና መራራ ቂም መነሻ ሆኖ ይቆጠራል።
ከሳምንታት በፊት የደጃዝማች ፀሐዩ ዕንቆሥላሴን የልማት ጉልበትና የጀግንነት ጽናት ሳቀርብ አንዱን ከሃይማኖቸኝነታቸው፣ሌላውን ከአርበኛ ቤተሰባቸው ለማሳየት ሞክሬ ነበር። አሁን ደግሞ እሳት ሆኖ በተወለደው የደርግ መንግሥት ውስጥ የደርግ አባል የነበሩት የመቶ አለቃ ጴጥሮስ ገብሬ ጥንካሬና ልልነታቸውን ማንሳት አስፈልጎኛል።
የእኒህን ሰው ታሪክ ተጠግቼ እንዳይ፣እንድሰማና እንድፈትሽ ያደረገኝ፣ባዮግራፊ የምጽፍበት አጋጣሚ ነበርና ለትውልድ ግብዐትና እርሾ ሊሆኑ ይችላሉ ያልኳቸውን ነጥቦች አጋራለሁ።
ሰውዬው፣በተደጋጋሚ በተጻፉት መጻሕፍት፣ማለትም በኮሎኔል መንግሥቱ ኀይለማርያም፣በኮሎኔል ደበላ ዲንሳና “ነበር”በተሰኘው በዘነበ ፈለቀ መጽሐፍና በሌሎቹ 4ኛ ክፍለጦር ደርግ ይሰባሰብባት በነበረች አዳራሽ ፣ገና በቅጡ ያልተግባቡት አባላት ሊበተኑ በነበረ ጊዜ፣ኤም ፎርቲኑን አውጥቶ”እያንዳንድህ ተመለስና ተቀመጥ፤ወዴት ልትሄዱ ነው?ማን ያቦካውን ማን ይጋግራል?”በማለት ደርጉን ከመፍረስ አድነውታል።
ደርጉ ሊበተን የነበረው” አየር ኀይሉ በጄት፣ክብር ዘበኛ በመድፍ የስብሰባ አዳራሹን ሊመታ ነው”በሚል ሴራ ተቃዋሚዎች ሊበትኗቸው ባሴሩት ሴራ ምክንያት ነበር። ይሁንና በዚህ ሰዐት ሊቀ መንበር መንግሥቱ ኀይለማርያም ከወንበራቸው ንቅንቅ አላሉም ነበር።
እንግዲህ አንዱ የጴጥሮስ ገብሬ ቆራጥነት የተወራበት ጊዜ ይህ ነበር። ከዚያ በፊት ግን ስለጴጥሮስ የማውቀው፣ኀይለኝነታቸውን ብቻ ነው። “ጫት ስትቅም መንገድ ላይ ካዩህ በሽጉጥ አፈሙዝ ጉንጭህን ገፍተው ያስተፉሀል” ይባል ነበር። ይሁንና በኋላ እንዳገኘሁት መረጃ፤ ጴጥሮስ የሲዳሞ ክፍለ ሀገር የደርጉ ተጠሪ በነበሩበት ሰዐት፣ሚሊሽያ አሠልጥነው በንጉሡ ከሥልጣን መውረድ ያኮረፉ የፊውዳሉ ሥርዐት ሽፍቶችን ተዋግተዋል። በሶማሊያው ወረራ ታጠቅ ጦር ሰፈር ከማሠልጠን ባለፈ እስከ ግንባር ዘምተው ተዋግተው፣አዋግተዋል።
በዚህም ጊዜ በጉዞ ላይ ሳሉ ሔሊኮፕተር ብልሽት ገጥሞት በመውደቁ፣ጆሯቸውን ተጎድተው ውጭ ሀገር ድረስ ሄደው ታክመዋል። በሌላም በኩል፣ በወቅቱ የሀገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ዐይን የነበረውን የቡና ንግድ በኮንትሮባንድ ሲያባክኑ የነበሩ ሰዎችን በመከታተል ችግሩን በከፍተኛ ደረጃ ቀንሰው የወረሱትን ቡና ለሕዝብ አገልግሎት እንዲውል አድርገው ነበር።
ተጨማሪ ያንብቡ

https://t.ly/wYnBs

Addis Admass

01 Dec, 20:56


ጨቅላ…እንደተወለደ…ቀዶ ህክምና ሊደረግለት ይችላል፡፡

አንድ ቤተሰብ ልጅ ሲያፈራ ለተወሰኑ ወራት ህጻኑን እንደተሰባሪ እቃ መመልከት የተለመደ ነው፡፡ ህጻኑ እንዳይቀጭ፤ብርድ እንዳይመታው፤ትን እንዳይለው፤እንዳይታፈን የሚ ለው ጥንቃቄ ይደረግለታል፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ ግን ይህ ገና ከማህጸን የወጣ ህጻን የአፈጣ ጠር ጉድለት ቢገጥመው 24/ሀያ አራት ሰአት ሳይሞላው ወደ ቀዶ ህክምና የሚገባበት አጋጣሚ አለ፡፡ ያ እንጭጭ ገላ እንዴት ስለትን ይችላል? የሰመ መን ወይንም የማደንዘዣውን ጉዳይ እንዴት ይወጣዋል ስንል ወደ ባለሙያ አመራን፡፡ ያነጋ ገርናት ዶ/ር ትሁት ተሾመ የህጻናት የሰመመን ወይንም የአንስቴዥያ ህክምና እስፔ ሻሊስት ናት፡፡ ዶ/ር ትሁትን ያገኘናት ኪዩር ከተሰኘ ሆስፒታል በስራ ላይ እያለች ነው፡፡ የሰጠችንን ማብራሪያ እነሆ ብለናል፡፡
ኪዩር የተሰኘው ሆስፒታል የሚገኘው ስድስት ኪሎን ወይንም አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን አለፍ ብሎ ወደ ቀኝ በመታጠፍ የሚገኝ ነው፡፡ ኪዩር ሆስፒታል ህክምናውን የሚሰጠው በነጻ ነው፡፡ ህክምናው ብቻም ሳይሆን የታካሚውም ሆነ የአስታማሚው ምግብ ጨምር በነጻ ይቀርባል፡፡ ኪዩር ሆስፒታል የአጥንትና የፕላስቲክ ቀዶ ህክምና ላይ የሚያተኩር ሆስፒታል ነው፡፡ በተለይም የተሰነጠቀ ከንፈር፤ላንቃ ያላቸው፤በቃጠሎ ምክንያት እጃቸው ወይንም እግራቸው የታጠፈ ወይንም የተጣመመ፤ በሚደርስባቸው ጉዳት ምክንያት ለመተንፈስ ወይንም አይና ቸውን ገልጠው ለማየት የማይችሉ ትን የፕላስቲክ ቀዶ ህክምና እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡ ከዚህ ውጭ ደግሞ የአጥንት ህክምና ያገኛሉ፡፡ ልጆች ሲወለዱ አጥንታቸው ተጣምሞ ወይንም ሌሎች የአካል ጉድለት ደርሶባቸው የሚወለዱ ከሆነ የህክምና እርዳታ ያገኛሉ፡፡ ጨቅላዎቹ ሲወለዱ የጀርባ አጥንት ክፍተት ወይንም መጣመም ካላቸው ሀያ አራት ሰአት ሳይሞላቸው ቀዶ ህክምናው ይደረጋል፡፡ በአጠቃላይም ጨቅላዎችም ሆኑ ህጻናት በአደጋም ይሁን በተፈጥሮ የሚደርስባቸውን የአካል አለመስተካከል እንደየሁኔታው ህክምና በማግኘት የሚስተካከሉበትን ቀዶ ህክምና አገልግሎት የሚሰጥ ሆስፒታል ነው፡፡ ኪዩር በአንድ አመት ከ ሶስት ሺህ እስከ ሶስት ሺህ አምስት መቶ (3000-3500) ለሚሆኑ ህክምና ይሰጣል፡፡ ይህን ህክምና የሚያገኙት ሁሉም ህጻናት ናቸው፡፡ ታካሚዎች ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች ይመ ጣሉ ማለት ይቻላል፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ

https://t.ly/nE2ay

Addis Admass

01 Dec, 20:54


https://t.ly/TrRr-

Addis Admass

01 Dec, 20:14


https://youtu.be/UQ-iscI4QMQ

Addis Admass

30 Nov, 19:52


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሰጠ
**

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዛሬው ዕለት አዳዲስ ሹመቶችን ሰጥቷል።

በዚሁ መሰረት:-
1. አቶ ግርማ ሰይፉ - የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ኃላፊ
2. ወ/ሮ ቆንጂት ደበላ - የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር
3. ወ/ሮ ኒዕመተላህ ከበደ⁠ - የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ
4. ወ/ሮ ይመኙሻል ታደሰ - የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ስራ አስኪያጅ
5. ⁠⁠አቶ ሙባረክ ከማል - የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ
6. አቶ ሁንዴ ከበደ - የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የባህል ዘርፍ ምክትል ኃላፊ
7. አቶ ታረቀኝ ገመቹ - የንግድ ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ ሆነው መሾማቸውን የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።⁠

Addis Admass

30 Nov, 13:21


የፈረንሳይ የአውሮፓ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብሔራዊ ሙዚየምን ጎበኙ
***

የፈረንሳይ የአውሮፓ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጂያን-ኖኤል ባሮት ብሔራዊ ሙዚየምን እና ሊሴ ገብረ ማሪያም ትምህርት ቤትን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ላይ የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

ኢትዮጵያ የረዥም ዘመን ታሪክ ያላትና የጥንታዊ ስልጣኔ ባለቤት መሆኗን የቱሪዝም ሚኒስትሯ አውስተዋል፡፡

የፈረንሳይ የአውሮፓ እና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጂያን-ኖኤል ባሮት በበኩላቸው ፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ሁሉን አቀፍ ትብብር ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላት መግለጻቸውን ከቱሪዝም ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1960ዎቹ ከመልካ ቁንጥሬ መካነ ቅርስ ለምርምር ወደ ፈረንሳይ ሀገር ተወስደው የነበሩ ጥንታዊ የሰው ዘር መገልገያ መሣሪያዎችን ለቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ አስረክበዋል፡፡

Addis Admass

30 Nov, 13:15


ብልፅግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጎች የወል እውነት ነው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
**************************

ኢትዮጵያ ከድህነት ለመውጣት ካላት ቁርጠኝነት አንጻር ፤ ብልፅግናን ማረጋገጥ የሁሉም ዜጎች የወል እውነት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስታውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓርቲም ህብረ ብሔራዊ ወንድማማችነት እንዲሁም እውነት፣ ዕውቀት እና ጥበብን መለያው አድርጎ ባለፉት አምስት ዓመታት ፈተናዎችን ወደ ድል በመቀየር በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገቡን ገልጸዋል፡፡

በፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና ማኀበራዊ ዘርፎች የተመዘገቡ ድሎችም የዜጎችን ተጠቃሚነት በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውን አመላክተዋል፡፡

በቀጣይ አምስት ዓመታት አዳዲስ ድሎችን በማስመዝገብ ከራሷ አልፋ ለሌሎች የምትተርፍ ሀገር ለመገንባት እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኀበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

Addis Admass

30 Nov, 13:11


በየዓመቱ ሕዳር 21 በድምቀት የሚከበረው የአክሱም ጽዮን ማርያም ዓመታዊ የንግሥ በዓል በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ እየተከበረ ነው።

ሐይማኖታዊ በዓሉን ለማክበር ወደ ከተማው ያቀኑ እንግዶች ከትናንት ጀምሮ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡

በዛሬው እለት እየተከበረ ባለው በዓል ወደ ከተማው የገቡ እንግዶች በበዓሉ ላይ እየታደሙ ነው፡፡

በክብረ በዓሉ ላይ የእምነቱ ተከታዮች፣ የሐይማኖት አባቶች እና የክልሉ ጊዜያዊ አሥተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

እንዲሁም ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች እና የውጭ ሀገራት የተገኙ እንግዶች በበዓሉ ላይ ታድመዋል።

Addis Admass

30 Nov, 13:09


https://youtu.be/QIHWxhCtgSc

Addis Admass

30 Nov, 09:38


የማዕከሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ኤሊዘር ሃይሌ፤ማዕከሉ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው፣ በኢትዮጵያውያን ሐኪሞች አገልግሎት እየሰጠ የሚገኝ የልብ ሕክምና ማዕከል መሆኑን ጠቁመው፤ በሕጻናት ላይ ለሚሰሩ 14 የሚደርሱ ስፔሻሊስት ሐኪሞች፣ በማዕከሉ ስልጠና እንደተሰጣቸው አመልክተዋል።

ከ1 ነጥብ 5 እስከ 2 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር ወጪ የሚደረግበትንና በውጭ አገር የሚሰጥ የልብ ቀዶ ጥገና ሕክምና ማስቀረት መቻሉን ዶክተር ኤሊዘር ያስታወቁ ሲሆን፤ ለዚህ ሕክምና የሚውሉ ግብዓቶች በአብዛኛው ከውጭ አገራት እንደሚመጡ ገልጸዋል።

"እነዚህን ግብዓቶች በሟሟላት አገልግሎቱ ቀጣይነት ይኖረው ዘንድ የኢትዮጵያውያን ድጋፍ ያስፈልገዋል" ብለዋል፣ ዶክተር ኤሊዘር። የተለያዩ ድርጅቶች ለማዕሉ ድጋፍ እንዲሰጡም ተጠይቋል፡፡

የማዕከሉ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ህሩይ ዓሊ ከአዲስ አድማስ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ግብዓቶችን ለመግዛትና ሌሎች ወጪዎችን ለመሸፈን ማዕከሉ የገንዘብ ውስንነቶች እንደገጠመው ጠቁመው፤ ከ80 በመቶ በላይ የሕክምና ግብዓቶችን ከውጭ አገራት እንደሚያስመጡ ተናግረዋል፡፡

“በአብዛኛው ከበጎ ፈቃደኛ ወገኖች ገንዘብ እያገኘን ነው፤ በተለይ ኢትዮ ቴሌኮም ጉልህ ድጋፍ እያደረገልን ነው” ብለዋል፤ዋና ሥራ አስፈጻሚው፡፡

“በጸጥታ ችግር ምክንያት ቀጠሮ የተሰጣቸው ታካሚዎች ወደ ማዕሉ እየመጡ አይደለም” ያሉት አቶ ህሩይ፤ ሌሎች ታካሚዎች ደግሞ በገንዘብ እጥረት ሳቢያ ሕክምናቸውን መከታተል አለመቻላቸውን ጠቁመዋል፡፡

Addis Admass

30 Nov, 09:38


“በጸጥታ ችግር ሳቢያ ቀጠሮ የተሰጣቸው ታካሚዎች
ወደ ማዕከሉ እየመጡ አይደለም”


“የገና ስጦታ ለልብ ህሙማን ሕጻናት” የተሰኘ እንቅስቃሴ ተጀምሯል

የኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ሕጻናት መርጃ ማዕከል፤ ”በጸጥታ ችግር ምክንያት ቀጠሮ የተሰጣቸው ታካሚዎች ወደ ማዕከሉ እየመጡ አይደለም” አሉ፡፡

የልብ ማዕከሉ፤ “የገና ስጦታ ለልብ ህሙማን ሕጻናት” በሚል መሪ ቃል፣ ለአንድ ወር ተኩል የሚዘልቅ እንቅስቃሴ መጀመሩን አስታውቋል።

ማዕከሉ ትላንት ሕዳር 19 ቀን 2017 ዓ.ም. በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በዚህ “የገና ስጦታ ለልብ ህሙማን ሕጻናት” የገቢ ማሰባሰቢያ ንቅናቄ፣ የተለያዩ በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦች፣ ድርጅቶችና ተቋማት ከወትሮው በተለየ መንገድ ማዕከሉን በዓይነትም ይሁን በገንዘብ የሚያግዙበት ነው ብለዋል፡፡

ይህን በማድረግ የልብ ሕክምና ለማግኘት ወረፋ የሚጠብቁ ከ8 ሺህ ላይ ህጻናት ህክምና እንዲያገኙ በማድረግ አጋርነታችሁን አሳዩ፤ ሲል ጠይቋል -ማዕከሉ፡፡

ከ500 እስከ 600 የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ለታካሚዎች እየተሰጠ መሆኑ ሲነገር፣ የተቋሙ ችግር በአንድ ጊዜ ድጋፍ ብቻ ሊፈታ እንደማይችል ተመልክቷል።

በመሆኑም የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትና ለአብነት ያህል ከዚህ ቀደም ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ነጻ የአየር ሰዓት ከመገናኛ ብዙሃን መገኘቱን በመግለጫው ተነግሯል።

Addis Admass

29 Nov, 10:49


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በየዕለቱ ሊበር ነው
***
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ኒውዮርክ ከተማ ሲያደርገው የነበረውን አራት ሳምንታዊ በረራ በማሳደግ በእየዕለቱ ሊበር መሆኑን አስታውቋል።
አየር መንገዱ ከህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ከተማዋ የሚያደርገውን እለታዊ በረራ እንደሚጀምር ባወጣው መረጃ አስታውቋል።

Addis Admass

29 Nov, 10:35


የጋሽ ማህሙድ ዝግጅት ያጫረብኝ ጥያቄ.......
የጋሽ ማህሙድን የምስጋናና የመድረክ ስንብት ትኬት ማለቅ ተከትሎ፣ አጠገቡ ለመገኘት ከአሜሪካ የተለያዩ ግዛቶችና ከአሜሪካ ውጪ ጭምር የሚደርሱን የስልክ ጥሪወች እጅግ በሚገርም ሁኔታ ብዙ ናቸው። ብዙ ጊዜ የመድረክ ዝግጅቶች ሲሰናዱ ያዘጋጆች ጭንቀት በቂ ሰው ይመጣ ይሆን ወይ የሚለው ነው። በዚህ የጋሽ ማህሙድ ዝግጅት ላይ ያየነው ግን ከዛ የተለየ ነው። እንዳውም “ራሱ ጋሽ ማህሙድም ትኬት አላገኘም” እየተባለ ተቀልዷል።
ይሄ ሁሉ የሆነው ግን ሌላ አዲስ ነገር ኖሮ፣ ታይቶ ተሰምቶ የማይታወቅ አርቲስት መጥቶ፣ ወይም አንዳች ታምር ተፈጥሮ አይደለም። ይሄ ሁሉ የሆነው ህዝቡ ለጋሽ ማህሙድ ባለው ፍቅር፣ በዚች መድረክን በሚሰናበትባት፣ በሚከበርባት፣ በሚመሰገንባት ምሽት አጠገቡ መሆን የታሪክ ባለቤት መሆን፣ መከበር ጭምር ስለሆነ ነው።
ጋሽ ማህሙድ ዘመን፣ ትውልድና ሁነት ከማይሽረው የሙዚቃ ብቃቱ በተጨማሪ፣ ግሩም የሆነ ስበዕናው፣ ደግነቱ፣ መልካምነቱ፣ የዋህነቱ፡ ብቻ ሰውነቱ በሁሉም ሰው ልብ ውስጥ እንዳስገባው ለመናገር ምስክር መጥራት አያስፈልግም።
ይሄ ክስተት ዛሬ ላይ እኛ እንዲህ ያለውን ክብርና ፍቅር የሚያስገኝ ስራ ምን ያህል እየሰራን ይሆን የሚለውን ጥያቄ አጭሮብኛል። አሁን ካለንበት ሞያ፣ ከምናገለግልበት ቦታ፣ ከወጣንበት ማማ፣ ከተሸከምነው ሃብት፣ ከደርብነው ዝና፤ ነገ ስንወርድ፣ ስንሰናበትና ስንለይ እንደጋሽ ማህሙድ በፍቅር እንሸኛለን ወይስ "ተገላገልን” እንባላለን? ሁላችንም ራሳችንን አጥብቀን መጠየቅ ያለብን ጥያቄ!
ዘመናችን በአገልግሎታችን፣ በጽናታችን፣ በበጎነታችንና በመልካም ስብዕናችን የተሰናሰለ ሆኖ ልክ እንደ ጋሽ ማህሙድ አይነት የፍቅርን በረከት ለእድሜ ማምሻችን ይሰንቅልን ዘንድ ጸሎቴና ምኞቴ ነው።

አበበ ፈለቀ

Addis Admass

29 Nov, 09:57


ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) አቶ መሐመድ እድሪስን የሰላም ሚኒስትር አድርገው ሾሙ
***********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አቶ መሐመድ እድሪስን የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር በማድረግ ሾመዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አቶ መሐመድ እድሪስን የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር በማድረግ መሾማቸውን አስታውቋል።

Addis Admass

29 Nov, 06:38


የአውስትራሊያ ፓርላማ ህጻናትን ከማህበራዊ ሚዲያ የሚያግድ አዋጅ አጸደቀ

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኔዝ ህጉ የወጣው ማህበራዊ ሚዲያው በወጣቶች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመከላከል ነው ብለዋል፡፡

አክለውም ‘‘ህጻናቶቻችን እንደ እድሜያቸው ልጅነቻውን እንዲኖሩ ነው የምንፈልገው፤ ወላጆችም እነሱን እያገዝን እንዳለ እንድገነዘቡ እንፈልጋለን፟’’ ብለዋል፡፡

ይሁንና የህጉ አተገባባር እንዴት እንደሆነ፣ በማህበራዊ ትስስርና ደህንነት ላይ ስለሚያስከትለው ጫና በአዋጁ ላይ አለመገለጹ ጥያቄ አስነስቷል፡፡

መሰል ህጎች ሲወጡ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ አይደለም፡፡ ባለፈው ዓመት ፈረንሳይ ከ15 እድሜ በታች ያሉ ህጻናት ያለ ወላጆቻቸው እውቅና ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ ፕላትፎርሙን የዘጋች ቢሆንም አሁን ላይ ግማሽ ያህሉ ተጠቃሚ ቪፒኤን መተግበሪያን በመጠቀም እግዱን እየተላለፉ መሆኑን የቢቢሲ ዘገባ ያመለክታል፡፡

በአሜሪካን ኡታህ በሚባል ስቴትም ከአውስትራሊያ ጋር የሚመሳሰል ህግ ለማውጣት የተሞከረ ቢሆንም በፌዴራሉ ዳኛ በኩል ህገ መንግስታዊ አይደለም በሚል ውድቅ ሆኗል፡፡

የአውስትራሊያ መንግስት በማህበራዊ ሚዲያው ላይ የወሰደው እርምጃ በበርካታ የዓለም መሪዎች ዘንድ የተወደደ ሲሆን ኖርዌይና ዩናይትድ ኪንግደም በቀጣይ ተመሳሳይ መንገድ ለመከተል የወሰኑ ሀገራት መሆናቸው ተገልጿል፡፡

Addis Admass

28 Nov, 21:13


የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ብዙ የዓለም አቀፍና የሃገር ውስጥ ችግሮችን ተቋቁሞ ትልቅ ለውጥ ማምጣቱን የምጣኔ ሃብት ባለሙያው አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ ገለፁ፡፡ የሩሲያና ዩኩሬን ጦርነት ያስከተለው የኢኮኖሚ ቀውስ፣ ኮቪድ 19፣ የሀገር ውስጥ ግጭቶችና ሌሎችም እክሎች ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ትልቅ ፈተናዎች እንደነበሩ ተናግረዋል፡፡

ባለፉት 5 ዓመታት የኢትዮጵያ አገር አቀፍ ምርት 92.6 ቢሊዮን ዶላር እንድነበር የሚያስታውሱት ባለሙያው፤ በነፍስ ወከፍ ደግሞ 840 ዶላር ነበር ብለዋል፡፡ የዋጋ ግሽበቱ ትልቅ እክል ቢፈጥርም፣ ይህን ለመፍታት ብሄራዊ ባንክ የወሰናቸው የተለያዩ ውሳኔዎች መኖራቸው አውስተዋል፡፡

የኢኮኖሚ ባለሙያው የአይኤምኤፍ መረጃን ጠቅሰው እንደተናገሩት፣ ባለፉት 5 ዓመታት በፍጥነት አደጉ ከሚባሉ የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ 1ኛ ደረጃን ይዛለች፡፡

Addis Admass

20 Nov, 21:09


የአቅርቦትና ፍላጎት አለመጣጣም፣ ስለመድኃኒቶቹ አጠቃቀም በማህበረሰቡ ውስጥ ያለው ግንዛቤ ዝቅተኛ መሆን፣ ወጥ የሆነ ጠንከራ ክትትልና ቁጥጥር ያለ መኖር በዋናነት የሚነሱ ችግሮች ሲሆኑ፤ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ግን ሁሉን አቀፍ ተግባራዊ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ ይነገራል፡፡

የጸረ ተህዋስያን መድኃኒት መላመድን ለመቀነስ ማህበረሰቡን በሁሉም የመገናኛ ዘዴዎች ተጠቅሞ ማስተማር፣ ማሳወቅና ማስገንዘብ አስፈላጊ ስለመሆኑም ይጠቀሳል፡፡

በምግብና መድኃኒትና ቁጥጥር ባለስልጣን የመድኃኒት መረጃና አጠቃቀም ዴስክ አስተባባሪ አቶ ኃይለማሪያም እሸቴ፤ በጸረ ተህዋስያን መድኃኒት አጠቃቀም ዙሪያ ማህበረሰቡ ያለው ግንዛቤ አናሳ በመሆኑ መድኃኒቶችን አላግባብ የመጠቀም ሁኔታ እየሰፋ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡

ባለስልጣኑ ከመድኃኒት አቅርቦት ባሻገር የክትትልና ቁጥጥር ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ የገለፁት ኃላፊው፤ የችግሩን መጠን ለመቀነስ እንዲያስችል መድኃኒት አቅራቢዎች፣ ተጠቃሚዎችና አምራቾች ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡

መድኃኒቶች ማዳን የማይችሉበት ደረጃ ቢደርሱ ምን ሊከሰት እንደሚችል መገመት ቀላል መሆኑን አንስተው፤ ሰው በየትኛውም መድኃኒት አጠቃቀም ዙሪያ የሀኪሙ የምርመራ ውጤትና ትእዛዝ፣ በቂ የፋርማሲ ባለሙያ ውሳኔ ሳይሰጥበት መጠቀሙ ተገቢ አለመሆኑን ይመክራሉ፡፡

ከህዳር 9 እስከ 15 የጸረ ተህዋስያን መድኃኒት በጀርሞች መላመድን ለመቀነስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሳምንት እናስተምር፣ እናሳውቅ፣ አሁን እንተግብር በሚል ሀሳብ በሀገር አቀፍ ደረጃ ይከበራል፡፡

Addis Admass

20 Nov, 21:09


የፀረ ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ለሰው ልጆች ስጋት እየሆነ ነው
በዓለም አቀፍ ደረጃ የጸረ ተህዋስያን መድኃኒቶች ያለ አግባብ ስራ ላይ በመዋላቸው መድኃኒቶቹ ከተህዋስያን ጋር በቀላሉ እንዲላመዱ እንደሚያስችላቸው ይገለፃል፡፡

በዚህም በየዓመቱ በጸረ ተህዋስያን መድኃኒት መላመድ ምክንያት በዓለማችን ከ1 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ለህልፈት ይዳረጋሉ፡፡

እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር በ2019 በኢትዮጵያ በገለልተኛ አካላት በተሰራ አንድ ጥናት ከ52 ሺህ በላይ ሰዎች መድኃኒቶችን አላግባብ በመጠቀማቸው ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸው ተገልጿል፡፡

በፀረ ተህዋሲያን መድሃኒቶች መላመድ ምክንያት ብዙ ዋጋ ተከፍሎባቸውና ዓመታትን ወስደው የተገኙ መድሃኒቶችን ዋጋ ቢስ የሚያደርግ ሲሆን በሽታውንም ለማከም አስቸጋሪ እንደሚያደርግ ይገለፃል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም እንደአብነት ቀዶ ሕክምና፣ ኬሞቴራፒና ሲ ሴክሽን እንዲሁም ሌሎች የህክምና ሂደቶችን የበለጠ አደጋ ውስጥ የሚጥል እንደሆነ የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡

Addis Admass

20 Nov, 21:07


አስተዳደራዊ ቅጣት አወሳሰድ
ቢሮዉ ወይም ጽሕፈት ቤቱ የተሰጠዉን ተግባር እና ኃላፊነት ወይም በደንቡ ላይ የተቀመጠዉን የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋም ግዴታ መሰረት በቁጥጥር ባለሙያ የተደረሰባቸዉ የህግ ጥሰት ሲኖር፡-
1. የቁጥጥር ባለሙያው ባከናወነው የቁጥጥር ተግባር ያገኘውን ውጤት በዚህ መመሪያ አባሪ ላይ በተያያዘ ቅፅ ና ቼክ ሊስት መሰረት አስፈላጊዉን መረጃ በመሙላትና ተጨማሪ መረጃ በማያያዝ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከውሳኔ ሃሳብ ጋር ለክትትልና ቁጥጥር ባለሙያ የቅርብ ኃላፊ 24 ሰዓት ውስጥ ያቀርባል፤
2. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀጽ (1) በተደነገገዉ መሰረት በቀረበዉ የክትትል እና ቁጥጥር ዉጤት መሰረት በደንቡ አንቀጽ 18 መሰረት እንደ ጉዳዩ አፈፃፀም ወይም አግባብ ወይም የጥፋት ድግግሞሽን መሰረት በማድረግ ቢሮዉ ወይም ጽሕፈት ቤቱ አማካኝነት አስተዳደራዊ እርምጃ ይወስዳል፣ ዉሳኔዉን ተግባራዊ ያደርጋል፡፡

Addis Admass

20 Nov, 21:00


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የባህል፣ ኪነ-ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ባለሙያዎች የደንብ ልብስ አለባበስ ደንብ ቁጥር 178/2016 መሰረት ክልከላ እና አስተዳደራዊ ቅጣት አወሳሰድ እንደሚከተለው ተጠቅሷል፡፡
ክልከላ!!
በዚህ መመሪያ ክፍል ሦስት ስለደንብ ልብስ አለባበስ፤ የጌጣጌጥ እና የመዋቢያ አጠቃቀም ከተደነገገው ውጭ አገልግሎት መስጠት የተከለከለ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ በማንኛውም የሆቴልና መሰል አገልግሎት ሰጪ ተቋም፡-
1. ከደንብ ልብሱ በላይ ሌላ ተደራቢ፣ ከተፈቀደው ውጭ ቀላቅሎ መልበስ፣ ከሸሚዝ ስር ረዥም የሚታይ ልብስ መልበስ፤
2. የደንብ ልብሱን ሳያሟሉ መልበስ፤
3. የሸሚዙን ቁልፍ ክፍት ማድረግ፣ ሸሚዙን ከሱሪ ወይም ከቀሚስ ወደ ውጪ ማድረግ፤
4. የእጅ ጣት ጥፍር ማሳደግ፣ ቀለም መቀባት ወይም ጥፍር ልጥፍና ሙሌት መሰራት፤
5. ማንኛውም ዓይነት በህክምና ያልታዘዘ መነጽር ማድረግ፤
6. የደንብ ልብሱን ንጽህና ሳይጠብቁ ወይም ሳያስተኩሱ መልበስ፤
7. ማንኛውም ዓይነት የከንፈር ቀለም ያለዉ ቻፒስቲክ ወይም ሊፒስቲክ መቀባት፤
8. ባለሙያዎቹ የለበሱት ቀሚስ ከሆነ ቅዱ ከኃላ ያልሆነ የለበሰ፡፡
⬇️

Addis Admass

20 Nov, 20:54


በመኖር አጸድ ውስጥ
(በእውቀቱ ስዩም)
ጊዜ ከሰው መሀል- መርጦ ሲያቀማጥል
ማጣት አለ ደሞ፥
የወለዱትን ልጅ፥ ጉድፍ ላይ የሚያስጥል
በተፈሰከ ቀን፥ ጾምን የሚያስቀጥል::
እድልና ትግል በሚጫወቱበት
በደልዳላው ስፍራ
አለቃና ጭፍራ-
-ቃል ሲለዋወጡ፥ ውልና መሀላ
“አብረን እናድጋለን” ቢባል ለይስሙላ
ወንዙን ሳያጎድል ፥ሐይቁ መች ሊሞላ፤
ጸሐይ ብትወጣ
ፍጥረት በጠቅላላው ጸጋዋን ቢቀበል
የደመናም ጠበል፥
ለሁሉ ቢደርስም
አንደኛው አያድግም፥ አንዱን ሳያከስም::

Addis Admass

20 Nov, 20:52


በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የመሪ ሉቄ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የወንጀል ምርመራ ማስተባበሪያ ኃላፊ ኢንስፔክተር ሰለሞን አበበ እንደገለፁት የግል ተበዳይ ተጠርጣሪዋን ለስራ ሲቀጥሯት ያቀረበችው የተያዥ ፎርም የራሷን ፎቶ በትክክል እንዳይለይ አድርጋ የለጠፈች ሲሆን የግል ተበዳይም ይህንን ሳያረጋግጡ በእምነት የቀጠሯት መሆኑን ገልፀው ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ በአጋዥነት መቅጠሩ ተገቢ ቢሆንም በህጋዊ መንገድ በቂ ተያዥ በማስቀረብ የተያዣቸውን አድራሻና ማንነት በአግባቡ በማጤን መቅጠር እንደሚገባና ውድ የሆኑ ንብረቶችንና ገንዘቦችን ደህንነቱ በተጠበቀ ቦታ በማስቀመጥ በተገቢው ሊቆጣጠሩና ንብረታቸውን ከስርቆት ወንጀል ሊታደጉ እንደሚገባም ተናግረዋል። ዘጋቢ ፦ዋና ሳጅን አዳነ
*

Addis Admass

20 Nov, 20:51


በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ከምትሰራበት ቤት ከ2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት እና ገንዘብ ሰርቃ የተሰወረች ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር መዋሏን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገለፀ።
***
ተጠርጣሪዋ ወንጀሉን የፈጸመችው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 አያት ዞን1 ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ/ም ነው፡፡ ተጠርጣሪዋ በደላላ አማካኝነት በቤት ሰራተኝነት ከተቀጠረችበት መኖሪያ ቤት በሶስተኛው ቀን ቆይታዋ የግል ተበዳይ ወደ ስራ በሄዱበት ወቅት አጋጣሚውን በመጠቀም በቤቱ ውስጥ የተቀመጠውን የተለያዩ ሀገራት ገንዘቦች እንዲሁም የተለያዩ የወርቅ ጌጣጌጦችን ሰርቃ በመሰወሯ የግል ተበዳይ የተፈፀመባቸውን የወንጀል ድርጊት ለመሪ ሉቄ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ አመልክተዋል፡፡
ተጠርጣሪዋ የወንጀል ድርጊቱን ከፈፀመች በኋላ የግል ተበዳይ ጋር ከመቀጠሯ በፊት በክፍለ ከተማው ወረዳ 14 አባዶ አካባቢ ኮንዶሚኒየም ቤት ለሦስት ወራት ተከራይታ በነበረበት ቤት ተደብቃ በክትትል የፖሊስ አባላት ከሰረቀቻቸው የተለያዩ አልባሳት፣ የተለያዩ የሴትና የወንድ ጫማዎች፣ 18 ሺህ የአሜሪካ ዶላርና የህንድ ሩፒ፣ የተለያዩ የወርቅና ልዩ ልዩ ጌጣጌጦች ጋር በቁጥጥር ስር መዋሏን ከክ/ከተማው የተገኘው መረጃ ያስረዳል። በተጨማሪም በሁለት የተለያዩ ስሞች የነዋሪነት መታወቂያ እንደተገኘባትም ተገልጿል።

Addis Admass

20 Nov, 20:44


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተከትሎ ከፍተኛ መነቃቃት ካሳዩ ዘርፎች አንዱ የማዕድን ዘርፍ ነው። በተለይ በወርቅ ምርት ላይ የታየው መነቃቃት ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው። በጋምቤላ ክልል ስራ የጀመረው ''ኢትኖ ማይኒንግ'' የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካ የኢትዮጵያን የማዕድን አቅሞች ወደ ልማት ለመቀየር ለተጀመረው ጉዞ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው።

Addis Admass

20 Nov, 20:33


የማህበረሰቡን እሴት ባልጠበቀ መልኩ መካነ መቃብር ቦታ በመሄድ ሙዚቃ ከፍተው ሲጨፍሩ የነበሩ ቲክቶከሮች ተያዙ። Addis Ababa Police

Addis Admass

20 Nov, 20:29


ከሩሲያ  የሶፍትዌር ኩባንያ  የስራ እድል ያገኘው የ7 ዓመቱ ህጻን

የሰባት አመቱ ኮዲንግ ባለሙያ ሰርጌይ ከሩሲያ የሶፍትዌር ኩባንያ ፕሮ32 አስተዳደር ቡድንን እንዲቀላቀል የስራ ግብዣ ቀርቦለታል፡፡

ታዳጊው ‘የኮዲንግ ሞዛርት” የሚል ቅጽል ስም የተሰጠው ሲሆን በዩቲዩብ ላይ በሚያቀርባቸው የፕሮግራሚንግ የማስተማሪያ ቪዲዮዎች ታዋቂነትን ያተረፈው ሰርጌይ በኮዲንግ ብቃቱ እና በማስተማር ችሎታው አድናቆትን አትርፏል።

ይህንን ተከትሎ የሩሲያ የሶፍትዌር ኩባንያ  ፕሮ32 ማሰልጠኛ ኃላፊ ሆኖ ድርጅቱን እንዲቀላቀል የስራ ቅጥር ደብዳቤ ልኮለታል።

ነገር ግን በሩሲያ ህግ መሰረት አንድ ሰው ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ ለመስራት እድሜው 14 አመት መድረስ አለበት፡፡

ስለዚህም ሰርጌይ እድሜው ለቅጥር እስከሚደርስ ድረስ ድርጅቱን ማገዝ በሚችልበት ሁኔታ ዙሪያ ከወላጆቹ ጋር መወያየቱን የፕሮ32 ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢጎር ማንዲክ ለቢቢሲ ወርልድ ሰርቪስ ተናግሯል፡፡

ቤተሰቦቹ ልጃቸው ባገኘው እድል በጣም ደስተኛ እንደሆኑ እና ሰርጌይ ኩባንያውን እስኪቀላቀል በጉጉት እንደሚጠብቁ ገልጸውልኛል ብሏል፡፡

ታዳጊው ሰርጌይ 3ሺህ 500 ተከታዮች ባሉት የዩትዩብ ቻናሉ ላይ በሩሲያኛ እንዳንዴም በተሰባበረ በእንግሊዘኛ በሚለቃቸው ስለኮዲንግ፣ ፓይቶን፣ ፕሮግራሚንግ፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ስለ ተለያዩ ቴክኖሎጂዎች በማስተማር ‘የኮዲንግ ሞዛርት’ ለመባል ችሏል፡፡ AddisWalta

Addis Admass

20 Nov, 20:19


የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት‼️
በከያኒት ዓለም ፀሐይ ወዳጆ በመታደስ ላይ የሚገኘውን የቢትወደድ ኃ/ጊዮርጊስ ኃ/ሚካኤል የቀድሞ መኖሪያ ቤት፣ የመጀመሪያው የማዘጋጃ ቤት፣ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት፣ ከ119 ዓመታት በፊት የተገነባውንና ለእቴጌ ጣይቱ የባህልና ትምህርት ማዕከል ሆኖ የሚያገለግል የቅርስ ቤት እድሳት ጎብኝተናል።
ከያኒት ዓለም ፀሐይ እያደረገች ላለችው ተምሳሌታዊ ሥራ እያመሰገንኩ አብዛኛውን እድሳት በጥሩ ሁኔታ በመስራት ላይ የምትገኝ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ደግፈን በተሻለ ሁኔታ ለቱሪስት መስህብነት እና ለታለመለት አላማ እንዲውል እናደርጋለን።
ትናንት ወረት መሆን የሚችሉትን ከዛሬ ጋር በማስማማት ለነገ እንዲተላለፍ በማለት ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን በቤተ መንግስትና በመላዉ ሀገራችን ያሉትን በማልማትና በሀገራችን ያሉ ቅርሶች በተገቢው መንገድ በማደስ ባስጀመሩን መሰረት እንደ አዲስ አበባ ጥንታዊ ቅርሶችን ከዛሬ ጋር በማስተሳሰር ለነገ ለማሻገር እድሳት የሚፈልጉት እድሳት በማድረግ በማዘመን ለቱሪዝም በሚያገለግል መልኩ በማስተዋወቅ፣ ሀብት ለማፍራት እንዲሁም ለትውልድ እንዲተላለፍ ተገቢውን ትኩረት ሰጥተን ከአራት ኪሎ እስከ ፒያሳ የሚገኙ ቅርሶችን በአዲስ መንገድ በልዩ ሁኔታ በኮሪደር ልማት ስራችን አድሰናል።
ማደስ፣ ማዘመን፣ ማስተዋወቅ፣ ቱሪዝምን በመጠቀም ሀብት መፍጠር እንዲሁም ትውልድ እንዲማርበት ማቆየት ተገቢ ሲሆን ያረጀ እና አሮጌው ሁሉ ቅርስ ባለመሆኑ ፈርሶ ዘመኑን በሚዋጅ ደረጃ ማልማት አስፈላጊ ነው።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

Addis Admass

20 Nov, 08:53


https://youtu.be/zq4ehojWKWs

Addis Admass

20 Nov, 08:24


https://t.ly/qK6SZ

Addis Admass

20 Nov, 07:30


https://t.ly/_fJKE

Addis Admass

17 Nov, 20:26


ሀገርን በማነፅ ጉዞ ውስጥ ጥበብ ዓይነተኛ ሚና አላት፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
**************

ዲጂታላይዝ የተደረገው በኢትዮጵያ የመጀመሪው ባለ ቀለም ፊልም "አስቴር" ዛሬ በአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በይፋ ተመርቋል።

ፊልሙ የሀገሪቱ አንጋፋ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችና ተጋባዥ እንግዶች በታደሙበት በአድዋ ሲኒማ ለእይታ ቀርቧል።

ይህን ተከትሎ ከንቲባ አዳነች በማኅበራዊ ትስስር ገፃቸው ባጋሩት መልዕክት፥ ሀገርን በማነፅ ጉዞ ውስጥ ጥበብ ዓይነተኛ ሚና አላት ብለዋል።

ዘርፉ የሀገሪቱን የልዕልና ጉዞ እንዲያሳልጥ ለማስቻል የከተማዋ አስተዳደር የኪነ-ጥበብ መሰረተ ልማቶችን ገንብቶ ለህዝቡ ጥቅም ማዋሉን ከንቲባዋ አውስተዋል።

የመዲናዋ አስተዳደር መሰል መሰረተ ልማቶችን የማስፋፋቱን ስራ ወደፊትም ይበልጥ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ቃል ገብተው፤ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎች ዕድሉን እንዲጠቀሙበት ጥሪ አቅርበዋል።

Addis Admass

17 Nov, 13:10


አቢሲንያ የበረራ አገልግሎት ማሰልጠኛ አካዳሚ ያሰለጠናቸውን አብራሪዎች በስካይላይት ሆቴል እያስመረቀ ነው።

Addis Admass

17 Nov, 10:15


መርካቶ ሽንኩርት በረንዳ ቃጠሎ ተነስቷል

Addis Admass

16 Nov, 13:08


የ58 ዓመቱ የዓለማችን ታላቁ ቦክሰኛ
ማይክ ታይሰን ከባድ ሽንፈት ገጠመው


ከ19 ዓመታት በኋላ የቦክስ ሪንግ ውስጥ የገባው የዓለማችን የሁለት ጊዜ የከባድ ሚዛን ሻምፒዮናው የ58 ዓመቱ ማይክ ታይሰን፣ በ27 ዓመቱ ተፋላሚው ጃክ ፖል በከፍተኛ የነጥብ ልዩነት ተሸነፈ።
ታይሰን በ70 ሺህ የቦክስ አድናቂዎቹና በኔትፍሊክስ በተከታተሉ ሚሊዮን ተመልካቾች ፊት ትላንት በቴክሳስ በተካሄደው ፍልሚያ፣ በሰፋ የነጥብ ልዩነት በመሸነፍ የቦክስ ሌጋሲው ላይ ጥላ አጥልቷል ተብሏል።

ከዩቲዩብርነት ፊቱን ወደ ቦክስ ያዞረው የ27 ዓመቱ ፖል፤ የቦክስ ጀማሪ ቢሆንም ወጣትና ስፖርተኛ ነበር። በዚህም ምክንያት በስምንት ዙር የሁለት ደቂቃ ዙሮች ውድድር ታይሰንን በሰነዘራቸው ከባድ ቡጢዎች በሰፋ ልዩነት አሸንፎታል። ታይሰን በበኩሉ፤ ላለፉት 19 ዓመታት ከቦክስ እርቆ ነበር የቆየው፡፡

የ58 ዓመቱ ታይሰን በፍልሚያው ወቅት የድሮው ቀልጣፋነቱና ንቃት አለመታየቱ የተነገረ ሲሆን፤ ዘገምተኛ ይመስል ነበር ተብሏል፡፡ ከግጥሚያው በፊት የጀግና አቀባበል የተደረገለት ታይሰን፣ ውድድሩ ወደ ማጠናቀቂያው ሲቃረብ ግን ብዙ ጉምጉምታዎችና ተቃውሞዎች ተሰምተዋል። የተወሰኑ ደጋፊዎችም ዳኞች ነጥቡን ይፋ ከማድረጋቸው በፊት ጥለው ወጥተዋል፡፡ ታይሰን በሁሉም ዙር በአጠቃላይ ማሳረፍ የቻለው 18 ቡጢዎችን ብቻ ሲሆን፤ ፖል ደግሞ 78 ቡጢዎችን ሰንዝሯል።

ፖል ዝነኛ የሆነው በኦንላይን በሚለቃቸው የፕራንክ ቪዲዮዎች ሲሆን፤ ወደ ቦክሱ ዓለም ከመቀላቀሉ በፊት 70 ሚሊዮን ተከታዮች ነበሩት ተብሏል።

Addis Admass

15 Nov, 20:02


ውድ አንባቢያን

ሳምንታዊ የቅዳሜ ጋዜጣችሁን አዲስ አድማስን፣ በእነዚህ
የመዲናችን መፃሕፍት መደብሮች ውስጥ እንደምታገኙት
ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
• ጃፋር መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ)
• ክብሩ መፃሕፍት መደብር (ጥቁር አንበሳ፣ ትራኮን ህንጻ)
• እነሆ መፃሕፍት መደብር (አራት ኪሎ)
• ኢዞጵ መፃሕፍት መደብር (አቡነ ጴጥሮስ)
• አምደ መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ) አዲስ አድማስ የእርስዎና ቤተሰብዎ

Addis Admass

15 Nov, 19:55


የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
=====
አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx
ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv

Addis Admass

15 Nov, 19:54


የጸሎት የጤና ፋይዳዎች

በዛሬው ፈጣን ዓለም ውስጥ፣ ውስጣዊ ሰላምን ማግኘት ፈታኝ ሊሆን ይችላል። ሆኖም፣ ለብዙዎች ጸሎት መረጋጋትን ለማዳበርና ከትልቅ ነገር ጋር ለመገናኘት እንደ መንገድ ሆኖ ያገለግላል።

ጸሎት ከቃላት በላይ ነው። ወደ ውስጥ ለመመልከት፣ አእምሮን ለማረጋጋትና ልብን ለመክፈት ግብዣ ነው። በንግግር፣ በዝምታ በማሰላሰል፣ ጸሎት ለውስጣዊ ሰላም የተቀደሰ ቦታ ይሰጣል።

ጭንቀቶችንና ትኩረትን የሚከፋፍሉ ነገሮችን በመተው፣ ከራስዎና ከመለኮታዊው ጋር በጥልቀት በመገናኘት፣ ወደ ጥልቅ ጸጥታ ሁኔታ ውስጥ መግባት ይችላሉ።

ጸሎት፡-
1. ውጥረትን ይቀንሳል
2. ስሜታችንን መቆጣጠር ያስችለናል
3. የድባቴንና የጭንቀት መጠንን ይቀንሳል
4. የተሻለ አመለካከት ያጎናጽፋል
5. በራስ መተማመንን ይጨምራል
6. ከችግሮች ማገገምን ያፋጥናል
7. አላስፈላጊ ፍላጎቶችን ያስቀራል
8, ከሰዎች ጋር ያለንን ግንኙነት ያሻሽላል
9. የዕድሜ ዘመናችንን ይጨምርልናል
ወጥ የሆነ የጸሎት ልምምድ ለማዳበር፡-

1. የተወሰነ ጊዜን ይመድቡ
በማለዳ፣ ከመተኛት በፊት ወይም ጸጥ ባለ ጊዜ፣ በየቀኑ መደበኛ የጸሎት ጊዜ መርሐግብርን ያውጡ።
2. ቦታ ይምረጡ
ትኩረትን ከሚከፋፍሉ ነገሮች የፀዳ ለጸሎት ልዩ ቦታ ምረጡ።
3. ክፍትና ተቀባይ ይሁኑ
ጸሎትን በክፍት ልብና አእምሮ፣ መመሪያና ግንዛቤዎችን ለመቀበል ዝግጁ ይሁኑ።

(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም)

Addis Admass

15 Nov, 19:47


“የውጭ ባንኮች ወደ ፋይናንስ ዘርፉ ገብተው
እንዲንቀሳቀሱ እንጂ እንዲቆጣጠሩን አልተፈቀደም ”


የውጭ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ገብተው እንዲንቀሳቀሱ እንጂ፣ እንዲቆጣጠሩን አለመፈቀዱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ አቶ ማሞ ምህረቱ ተናገሩ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ፤ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ገለጻ የሰጡ ሲሆን፤ ከተለያዩ የባንክ ባለድርሻ አካላት ጋር ይፋዊ ውይይት አድርገዋል፡፡

በዚህ ወቅት የብሔራዊ ባንክ ገዢው ማሞ ምህረቱ፣ የውጭ ባንኮች ወደ ሀገር ውስጥ መግባታቸው በሚያመጣው እድልና ስጋት ዙሪያ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ፤ "ክፍት ማድረግ ማለት ተጨማሪ ተዋናዮችን መጋበዝ ሲሆን፣ እኛ ከቁጥጥር ነፃ እናድርጋቸው እያልን ሳይሆን፣ እየተቆጣጠርን ዘርፉን ክፍት እናደርጋለን ነው ያልነው" ብለዋል፡፡

አክለውም፤ የውጭ ባንኮች ወደ አገር ውስጥ መግባታቸው የፋይናንስ ጤናማነትን በጠበቀ መልኩ ለዘርፉ የተሻለ ተጠቃሚነትን ያመጣል ብለዋል።

የባንኮች ውህደትን በተመለከተ ለተነሱ ጥያቄዎችም ምላሽ ሰጥተዋል። “የባንኮች ውህደት አስገዳጅ አይደለም፤ እንደ መመሪያ ሥርዓት ታስቦ የተቀመጠ እንጂ፣ የፖሊሲ ውሳኔ አይደለም“ ሲሉ አቶ ማሞ ምህረቱ አብራርተዋል፡፡

መንግስት ኢኮኖሚውን ነፃ ለማድረግና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ መወሰኑን ተከትሎ ከኬንያ፣ ሞሮኮና የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፣ ባንኮች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት በዝግጅት ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡

Addis Admass

15 Nov, 18:24


የዛሬ 34 ዓመት የተሰራው “አስቴር” ፊልም
ወደ ዲጂታል ተቀይሮ ለዕይታ ሊቀርብ ነው

• ፊልሙ የፊታችን እሁድ ይመረቃል

በኢትዮጵያዊያን ባለሙያዎች ብቻ የተሰራው “አስቴር” የተሰኘ ፊልም ወደ ዲጂታል ተቀይሮ ለዕይታ ሊቀርብ መሆኑን የአዲስ አበባ ባህል፣ ኪነጥበብና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሒሩት ካሳው (ዶ/ር) ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቁ፡፡

በ1983 ዓ.ም በኢትዮጵያ ፊልም ኮርፖሬሽን አማካኝነት ሀገራዊ ዘውግ ላይ ተንተርሶ የተሰራውና "አስቴር" የተሰኘው ኢትዮጵያዊ ፊልም፣ የአጻጻፍ ደረጃው ከፍ ያለና ከድርሰት እስከ ፕሮዳክሽን ድረስ ሙሉ በሙሉ በሀገር ባለሙያዎች የተሰራ መሆኑን ሐላፊዋ ገልጸዋል፡፡

"አስቴር" ፊልም የዛሬውን የፊልም ኢንዱስትሪና የፈጠራ ክህሎት ለማሳደግ መነሻ መሆኑን የገለጹት ኃላፊዋ፤ ቢሮው በቴክኖሎጂ ምክንያት ለዕይታ ሳይበቁ የቆዩ ቀደምት የፊልም ሥራዎችን ከሦስት ዓመታት ወዲህ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በማፈላለግ ዲጂታላይዝድ እንዲሆኑ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ሒሩት ካሣው አክለው እንደገለጹትም፤ ቆየት ባሉ ፊልሞች የቀደመውን ማህበረሰብ የባህል ትስስር ለመዳሰስና ዛሬ ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ለመለየት፣ ቢሮአቸው ከዚህ በፊት የመጀመሪያውን ባለ ነጭና ጥቁር ቀለም "ሒሩት አባቷ ማነው?" የተሰኘ ፊልም በድጋሚ ለዕይታ እንዲበቃ ለሲኒማ ቤቶች አስተዳደር አስረክቧል፡፡

የዛሬ 34 ዓመት የተሰራው “አስቴር“ ፊልም፣ የፊታችን እሁድ ህዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 8 ሰዓት የፊልሙ ባለቤቶች፣ ተዋንያንና የኪነ ጥበብ አፍቃሪያን በታደሙበት በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም በይፋ ይመረቃል ተብሏል፡፡

Addis Admass

15 Nov, 17:44


በነገው የማጠቃለያና የምስጋና ፕሮግራም ላይ ከኔ ጋር ቡና እየጠጡ ለመጨዋወት በርካታ የአዲስ አበባ ዩንቨርሲቲ የቀድሞና የአሁኖቹ የቴአትር ተማሪዎች እንዲሁም የኪነጥበብ ባለሙያዎች እና ጋዜጠኞች ነገ ቅዳሜ ህዳር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋት 4:00-6:00 ሰዓት "ንቃ ቡና" ከእኔ ጋር የማይቀርበት ቀጠሮ ይዘዋል!!

ሌሎቻችሁም በዚሁ ፕሮግራም ላይ እንድትገኙ በማክበር እጠይቃለሁ!!! "

(ተሻለ አሰፋ)


አድራሻ:- "ንቃ ቡና"
ከአራት ኪሎ ወደ ፒያሳ በሚወስደው መንገድ፣
ከአራዳ ክፍለ ከተማ አጠገብ፤ አንግላ በርገር የሚገኝበት አንደኛ ፎቅ።

መረጃውን ለሌሎች #share ሼር በማድረግ ተባባሩን::

Addis Admass

15 Nov, 17:43


ዶ/ር ተሻለ አሰፋ ነገ ቅዳሜ የምስጋና ፕሮግራም አዘጋጅቷል!! ሁላችሁንም በክብር ጋብዟችኃል!!!
=============================

(ይትባረክ ዋለልኝ)

ዶ/ር ተሻለ አሰፋ የመፅሐፍ ሽያጭ ዘመቻ ማጠቃለያውን በማስመልከት የምስጋና እና የመፅሐፍ ማስፈረም ፕሮግራም ያደርጋል!! ይህንንም ፕሮግራም አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፏል::

" በቅርቡ ታትሞ ለንባብ የበቃውን "የተውኔት ዝግጅት መሰረታዊያን " የተሰኝውን መፅሐፌን ላለፉት ሁለት ሳምንታት የቅድሚያ ሽያጭ ማድረጋችን ይታወቃል:: በቅድሚያ በዚህ የመፅሐፍ ሽያጭ ላይ የተሳተፋችሁትን ሁሉ በጣም አመሰግናለህ:: እኔም ይህንን የቅድሚያ ሽያጭ ማጠቃለያ በማስመልከት ነገ ቅዳሜ ህዳር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 እስከ 6:00 ድረስ አራት ኪሎ "ንቃ " ቡና ባለፉት ሁለት ሳምንታት በሐገር ውስጥና በውጭ ሐገር ውስጥ ሆነው መፅሐፉን ለገዙኝ ኢትዮጵያውያን የምስጋና ዝግጅትና የመፅሐፍ ማስፈረም ፕሮግራም አደርጋለሁ!!
ስለመፅሐፉም ትንሽ ሃሳብ አጋራችኃለው::
እንዲሁም በቅድሚያ ለገዙ በስማቸው መፅሐፌን ፈርሜ በክብር እሰጣቸዋለሁ ::

Addis Admass

14 Nov, 20:05


ቢጂአይ ኢትዮጵያ ከ10 ሚ.ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን
የት/ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀክት አጠናቅቆ አስረከበ

ቢጂአይ ኢትዮጵያ በሐዋሳ ከተማ ጨፌ ቆንቦዬ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት፣ ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበትን የትምህርት ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀከት አጠናቅቆ በዛሬው እለት አስረክቧል፡፡

ከ10 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የማስፋፊያ ፕሮጀከት፤ ሰባት አዳዲስ የትምህርት ክፍሎችና ዘመናዊ የመጸዳጃ ቤቶችን በመገንባት የትምህርት ቤቱን ተማሪዎች የመቀበል አቅም በሚገባ አሻሽሏል ተብሏል።

የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ ትምህርት ቤቱ በአንድ ፈረቃ ከ525 በላይ አዲስ ተማሪዎችን በመቀበል እንዲያስተናግድም አስችሎታል፡፡

በስድስት ወራት ውስጥ የተጠናቀቀው የጨፌ ቆንቦዬ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት ማስፋፊያ ፕሮጀከት፤ቢጂአይ ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ በ2024 ዓ.ም ከ70 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ካደረገባቸው የማህበራዊ ኃላፊነት ድጋፎች ውስጥ አንደኛው እንደሆነ ተገልጿል፡፡

Addis Admass

14 Nov, 19:48


የ2017 ታላቁ ሩጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የፀጥታና
ደህንነት አካላት ዝግጅታቸውን ማጠናቀቃቸውን አስታወቁ


በኢትዮጵያ የሚካሄደዉ የ2017 ታላቁ ሩጫ ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ዝግጅታቸውን አጠናቅቀው ወደ ሥራ መግባታቸውን አስታዉቀዋል፡፡

በየዓመቱ በአዲስ አበባ ከሚደረጉ ስፖርታዊ ውድድሮች አንዱ የሆነው ታላቁ ሩጫ፣ ለ24ኛ ጊዜ የፊታችን እሁድ ሕዳር 8 ቀን 2017 ዓ.ም 50 ሺህ ተወዳዳሪዎች እንደሚሳተፉበትና መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በማድረግ እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡

የፀጥታና ደህንነት አካላት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ዋና መስሪያ ቤት የ2017 ታላቁ ሩጫ ሰላማዊ ሆኖ እንዲጠናቀቅ ከባለድርሻ አካላት ጋር ወይይት አድርገዋል፡፡

Addis Admass

14 Nov, 19:43


የስርቆትና የቅሚያ ወንጀል የሚፈፅሙ ተጠርጣሪዎች ተያዙ


ተሽከርካሪን በመጠቀም በተለያዩ ቦታዎች እየተንቀሳቀሱ ወንጀል ሲፈፅሙ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች በተደረገባቸው ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ የክትትልና ኦፕሬሽን ክፍል በቁጥጥር ስር ያዋላቸው ተጠርጣሪዎች፣ የተለያዩ ዘዴዎችን እየተጠቀሙ በተሽከርካሪ በመንቀሳቀስ፣ የስርቆትና የቅሚያ ወንጀል የሚፈፅሙ ናቸው ተብሏል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ሳሪስ አካባቢ በአንድ ግለሰብ ላይ ምራቅ በመትፋትና ምራቁን የተፉት ባለማወቅ እንደሆነ ተናግረው ይቅርታ በመጠየቅ፣ ምራቁን ከግለሰቡ ላይ የሚጠርጉ በመምሰል ከኪሱ ውስጥ ሞባይል ስልክ ሰርቀው በተለምዶ “ትፍታ” የሚባለውን ወንጀል ፈፅመው፣ በተሽከርካሪ ተሳፍረው መሰወራቸው ተጠቅሷል፡፡

በአዲስ አበባ ፖሊስ የክትትልና ኦፕሬሽን ክፍል አባላት ክትትል ሲደረግባቸው የነበሩት እነዚህ ተጠርጣሪዎች በድጋሚ ወደ ለገሃር አካባቢ በመምጣት ተመሳሳይ ወንጀል ለመፈፀም ሙከራ አድርገው ሲያመልጡ የክትትል አባላቱ ቸርችል ጎዳና አካባቢ በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ መረጃ ያመለክታል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ለወንጀል ተግባር የሚጠቀሙበት ተሽከርካሪ ሲፈተሽ፣ አራት ሞባይል ስልኮች መገኘታቸውን ፖሊስ ጠቅሷል። ከእነዚህ ስልኮች መካከልም አንዱ የህጻናት ፎቶ በእስክሪኑ ላይም የሚገኝ ሲሆን፤ በእነዚህ ተጠርጣሪዎች ወንጀል ተፈፅሞብኛል የሚል ግለሰብ አራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል በመቅረብ መረጃ መስጠት እንደሚችልም ተገልጿል፡፡

Addis Admass

14 Nov, 19:35


አጠቃላይ ለዚህ ፕሮጀክት ዕውን መሆን ያስፈልጋል ተብሎ የታቀደው በጀት 68 ሚሊዮን 997 ሺ 500 ብር እንደሆነ ተገልጿል። የ”የሺህ ጋብቻ” ፕሮግራም ያሜንት ከባሕልና ስፖርት ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ባሕል፣ ኪነ ጥበብና ቱሪዝም ቢሮ እና ከአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባና ደንበኞች አገልግሎት ኤጀንሲ ጋር እንዲሁም ከሌሎች የፌዴራልና የክልል መንግስታዊ ተቋማትና ከግል ባለድርሻ አካላት ጋር አብሮ በቅንጅት ይሰራል ተብሏል።

ያሜንት ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ከ2005 ዓ.ም. ጀምሮ የ”የሺሕ ጋብቻ” ፕሮጀክቶችንና የአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራሞችን ሲሰራ ቆይቷል፡፡ ዘንድሮ 3ኛውን የ”የሺሕ ጋብቻ” በመጪው ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም. በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚያከናውን ተገልጿል።

Addis Admass

14 Nov, 19:35


68 ሚ. ብር በሚጠጋ በጀት የሰርግ ሥነ ስርዓት ሊካሄድ ነው

• 1 ሺሕ 250 ጥንዶች ይሳተፉበታል ተብሏል


ያሜንት ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማሕበር ያዘጋጀው “የሺህ ጋብቻ” የሰርግ ስነ ሥርዓት 68 ሚሊዮን ብር በሚጠጋ በጀት ሊካሄድ መሆኑ ተገልጿል። በዚህ ሥነ ስርዓት ላይ 1 ሺሕ 250 ጥንዶች እንደሚሳተፉበት ተነግሯል።

ዛሬ ሕዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በሐርመኒ ሆቴል በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በዘንድሮ የ”የሺህ ጋብቻ” 2 ሺ 17 ኪሎ ግራም ባህላዊ ዳቦ እንደሚጋገር፣ 12 ሺ የሚደርሱ የቡና ሲኒዎች ያሉት የቡና እንጠጣ ፕሮግራም እንደሚካሄድ፣ በሙሽሮች ቁጥር ደግሞ 250 የሚደርሱ ከልዩ ልዩ የአፍሪካ አገራት የተውጣጡ ጥንዶች ከ1ሺህ ኢትዮጵያውያን ጥንዶች ጋር በድምሩ 1 ሺ 250 ጥንዶች ሰርጋቸውን የሚያደርጉ መሆኑ ተነግሯል።

የያሜንት ኢቬንትስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስናቀ አማኑኤል የ”የሺህ ጋብቻ” ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውን አስመልክቶ ሲናገሩ፤ ጥንዶች ለሰርግ ድግስ ሊያውሉ የነበረውን ከፍተኛ ወጪ (በገንዘብ፣ በጊዜና በጉልበት ወዘተ) በማስቀረት፣ የጥንዶችን ኢኮኖሚ ማጎልበት ለአጠቃላይ አገራዊ ቁጠባ የበኩላቸውን እንዲያበረክቱ “የራሱን ሚና መጫወት ነው” ብለዋል።

በተጨማሪም፤ የኢትዮጵያ ብሎም የአፍሪካ አገራት ሕዝቦችን የካበተ ባሕላዊ የሰርግ ስነ ስርዓት አጉልቶ ማሳየት እንዲሁም አዲስ አበባን የ”ሃኒሙን” ማዕከል ማድረግ እንደሆነ አቶ አስናቀ ገልጸዋል።

Addis Admass

14 Nov, 19:16


የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
=====
አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx
ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv

Addis Admass

14 Nov, 19:15


ኢትዮጵያ አልሻባብን በማዳከም እንደምትቀጥልበት አስታወቀች

በሶማሊያ በሚሰማራው አዲሱ የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍና የማረጋጋት ተልዕኮ ውጪ የተደረገችው ኢትዮጵያ፤ አልሻባብን በማዳከም ተግባር እንደምትቀጥልበት አስታወቀች።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው በዛሬው ዕለት ህዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ኢትዮጵያ የሶማሊያውን ታጣቂ ቡድን አልሻባብን ለማሽመድመድ ለዘመናት ያደረገችው ዘመቻ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

“አልሻባብ ብሄራዊ ደህንነታችን ላይ ስጋት የማይሆንበት ደረጃ እስኪደርስ እንዲሁም እስካሁን የተመዘገቡ ድሎች እንዳይቀለበሱ አልሻባብን ለማዳከም የተሰሩ ወሳኝ ስራዎች በማንኛውም መንገድ ይቀጥላሉ” ብለዋል፤ አምባሳደሩ፡፡

የሶማሊያ የሽግግር መንግሥት ወታደሮቿን እንድታስገባ ከጠየቀበት ጊዜ ጀምሮ ለአስራ ሰባት ዓመታት ያህል በአፍሪካ ኅብረት ጥላ ስር በሚገኘው የሰላም አስከባሪ ልዑክ አሰማርታ የምትገኘው ኢትዮጵያ፤ ሰራዊቷ በሶማሊያ ከሚሰማራው አዲሱ ተልዕኮ ውጭ መደረጉን ከሰሞኑ የሶማሊያ የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቆ ነበር።

የኢትዮጵያ ሰራዊት በአዲሱ የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍና የማረጋጋት ተልዕኮ እንዳይካተት መደረጉን አስመልክቶ የመንግሥታቸው አቋም ምን እንደሆነ ከጋዜጠኞች ለተጠየቁት ጥያቄ ቃል አቀባዩ ቀጥተኛ ምላሽ ባይሰጡም፣ ኢትዮጵያ ቡድኑን የማዳከም ተግባሯን ትቀጥልበታለች ብለዋል።
አምባሳደር ነቢያት በጋዜጣዊ መግለጫው ኢትዮጵያ ለቀጣናው ያደረገችውን አስተዋጽኦ ሲናገሩ፤ “አሸባሪው አልሻባብ በቀጣናው የጋረጠውን ስጋት በመግታት ረገድ ኢትዮጵያ እየተጫወተችው ያለውን ቁልፍ ሚና ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የሚያውቀውና የሚገነዘበው ነው” ብለዋል።

Addis Admass

14 Nov, 19:14


ፕሬዚዳንት ባይደንና ትራምፕ ለመጀመሪያ ጊዜ በዋይት ሃውስ ተነጋገሩ

ተሰናባቹ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ተመራጩን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለመጀመሪያ ጊዜ በዋይት ሃውስ ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን፤ በዋይት ሃውስ ቆይታቸው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ለ2 ሰዓታት የቆየ ውይይት ማድረጋቸው ተዘግቧል፡፡

ፕሬዚዳንት ባይደን ዶናልድ ትራምፕን “እንኳን በድጋሚ ተመልሰው መጡ” በማለት በነጩ ቤተ መንግስት አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ባይደንና ትራምፕ በመጀመሪያ ውይይታቸው፣ የሩሲያ- ዩክሬን ጦርነትና የመካከለኛው ምስራቅ ጉዳይን እንዲሁም ሰላማዊ የስልጣን ሽግግርን የተመለከቱ ጉዳዮችን ማንሳታቸውን ዋይት ሃውስ አስታውቋል።

ሁለቱ መሪዎች በተጨማሪም ወሳኝ በሆኑ ሀገራዊ ደህንነትና የሀገር ውስጥ ፖሊሲ ጉዳዮች ላይ መወያየታቸውም ታውቋል፡፡

በውይይቱ ወቅት ስለ ሩሲያ ዩክሬን ጉዳይ የተነሳ ሲሆን፤ በዚህም ላይ ፕሬዚዳንት ባይደንና ዶናልድ ትራምፕ የተለያየ አቋም አንጸባርቀዋል።

ፕሬዚዳንት ባይደን ዩክሬንን መደገፍ ለአሜሪካ ብሄራዊ ደህንነት የሚጠቅም መሆኑን ያነሱ ሲሆን፣ ተመራጩ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው፤ የዩክሬን ሩሲያ ጦርነት በአፋጣኝ መቆም እንዳለበት መናገራቸው ነው የተገለጸው።

Addis Admass

14 Nov, 12:19


ታዋቂው የሰብአዊ መብት ተሟጋች የኢራንን መንግሥት በመቃወም ራሱን አጠፋ

አራት የኢራን የፖለቲካ እስረኞች እስከ ረቡዕ ምሽት ከእስር ካልተለቀቁ ራሱን እንደሚያጠፋ በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ አስታውቆ የነበረው ታዋቂው ኢራናዊ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ኪያኖሽ ሳንጃሪ፤ የኢራንን መንግሥት በመቃወም ራሱን ማጥፋቱን ቢቢሲ ዘገበ፡፡

“አንድ ቀን ኢራናውያን ነቅተው ባርነትን ያሸንፋሉ” ሲል ራሱን ከማጥፋቱ በፊት በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መጻፉ ተነግሯል፡፡

የኢራንን መንግሥት አጥብቶ በመተቸት የሚታወቀው ኪያኖሽ ሳንጃሪ ለዴሞክራሲ ሲታገል የቆየ ሲሆን፤ ከመሞቱ በፊት “ማንም ሰው ሐሳቡን በመግለጹ ምክንያት መታሰር የለበትም። መቃወም የሁሉም ኢራናውያን መብት ነው” ብሏል።

ታዋቂው ታጋይ የኢራን መንግሥት እንዲፈታቸው የጠየቃቸው አራቱም ፖለቲከኞች የታሰሩት የ22 ዓመቷ ማሳ አሚኒ መገደሏን ተከትሎ፣ የተነሳውን ሕዝባዊ ተቃውሞ በመደገፋቸውና በመሳተፋቸው ነበር።

Addis Admass

14 Nov, 11:21


በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማት ላይ ስርቆት የፈፀሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ

• ከ5 ዓመት እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ሊቀጡ ይችላሉ

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ካዛንቺስ አካባቢ 550 ሺ ብር የሚገመት የኤሌክትሪክ መስመር ላይ ስርቆት ያደረሱ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ፡፡

በኤሌክትሪክ መሰረተ-ልማቶች ላይ ስርቆት መፈፀም፣ ከ5 ዓመት እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት ያስቀጣል፡፡

በቁጥጥር ስር የዋሉት ግለሰቦች በኮሪደር ልማት ሥራ ምክንያት ተቆፍረው የተቀመጡ 200 ሜትር የሚደርሱ የኤሌክትሪክ መስመሮችን ቆራርጠው ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ ሲሆን፤ ተቋሙ ከአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ጋር ባደረገው ከፍተኛ ርብርብ መያዛቸው ተጠቅሷል፡፡

በኤሌክትሪክ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚፈፀምን የስርቆት ወንጀል መከላከል የሁሉም ሃላፊነት በመሆኑ መሰል እኩይ ተግባራትን የሚፈፅሙ አካላትን ሲመለከቱ በአካባቢው ለሚገኙ የፀጥታ አካላት ማሳወቅና ጥበቃ ማድረግ ይገባል ተብሏል።

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሩብ አመት ብቻ ከ2.7 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የስርቆት ወንጀል መፈፀሙ ታውቋል፡፡

Addis Admass

14 Nov, 06:19


https://t.ly/1CFX_

Addis Admass

14 Nov, 06:15


የሁምናሳ ውልብታዎች

፨ ከዓለማየሁ ገላጋይ ‹ውልብታ› ስድስት ዓመት በኋላ በሀይሉ ገብረእግዚአብሔር (ሁምናሳ ገርቢቸ ረቢ) የማምሻ ውልብታዎችን ይዞልን መጣ። በ220 ገጽ ወደ 260 የሚጠጉ ወጎችን ሳቅን ለውሶ አቀረበልን። ‹‹ማምሻ ግሮሰሪ›› በሚል የተከፈተው የፌስቡክ ገጽ ላይ ያቀርባቸው የነበሩ ጽሑፎችን ‹ለሌላው ኅብረተሰብም ይደርስ ዘንድ ተመርጠውና ብርቱ ማስተካከያ ተደርጎባቸው› በአንድ ተጠረዙ። ዓለማየሁ ገላጋይ እንደሚለው፤ ዘመን የሚፈጥራቸው ቀልዶችና ምጸቶችን ሰብስበን ማስተላለፍ ወደፊት ዘመኑንና ህዝቡን እንድንረዳ ያስችላል። የማምሻ ወጎች በኃይሉ እንደ ታገል ሰይፉ ‹ዝንቡላ እና ካሮት›፣ እንደ ዓለማየሁ ገላጋይ ‹ወሪሳ› ሳቅን ለውሶ ሀዘንና ምሬታችንን ያቀረበልን፤ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ኂስ ነው። Birth of Tragedy ላይ ኒቼ እንደሚለው፤ ‹‹ሐዘንና መከራን የቀልድ መነሻ ማድረግ ያስፈልጋል፤ ካልኾነ ማበድ ይከተላልና።››... ሩሲያዊው ደራሲ አንቷን ቼኾቭም፤ ‹‹እንድቀልድና እንዳሽሟጥጥ ያደረገኝ የሐዘን መናኸሪያ መኾኔ ነው።›› ይላል። ሁምናሳም ሀዘንና ምሬቶቻችንን በመጠጥ ቤት አስተናጋጅነቱ ከተለያዩ ሠዎች የታዘበውን ያቀርብልናል። እንደዚህ ዓይነት ‹ወጎችን› መርምረን አይተን ዘመናችንን እንገነዘባለን። ‹ኢህአዴግን እከስሳለሁ› ላይ ዓለማየሁ ገላጋይ ‹‹ጥርስን ከመገሽለጥ ባለፈ የቀልዱን መሪር ዕውነታ ፈልፍሎ የሚያወጣና የቅሬታ ምርቱን የሚፈትን ህዝብ ማስፈለጉ የግድ ነው።›› (95) ይለናል።
፨ ሁምናሳ፤ የሰካራም፣ አስከሬን፣ አመንዝራ የሚሉ ስያሜዎች ከየት እንደመጡም ይነግረናል። ምን ስለ እኛ የማይነግረን ነገር አለ? ጥርስ የማያስከድኑ ወጎቹ ኅብረተሰባችንን፣ መንግሥታችን፣ ፖለቲካችንን፣ አስተሳሰባችንን ይወቅሳሉ (መብራትና ውኃ ኃይሎችም አይቀሩ)። ከሳቅን በኋላ ነው ሕመሙን የምንረዳው፤ ደግመን የምናነበውም። ሕመሙ ሲሰማን ስህተቶቹ እንዲሻሻሉ እንጥራለን። ‹‹በቀልድ ክንብንብ ውስጥ ያለው ማኅበረሰባዊ ሽሙጥ ስህተቶችን ለማረም እንደ ዓይነተኛ ጉዳይ ቦታ ያገኛል።›› (ኢህአዴግን እከስሳለሁ፣ 93)...
‹‹ መኖርም መሞትም የከበደብሽ፤
የነንጠቅ አገር ጦቢያ እንዴት ነሽ!?››(40)...፣ ‹‹እዚኽ አገር ፈጣሪ ሊጠብቅ ያልቻለው ወንድሙን ከወንድሙ ጥቃት ነው።››... እያለን ቆም ብለን እንድናስብ ያስታውሰናል።
፨ ከሁምናሳ ውልብታዎች ሀገራችንንና ፖለቲካችንን በምጸት የገለጸበትን ሦስት አራት እንጥቀስ፦
ቢራ በሳጥን የሚገዛ ደንበኛችንን፣ ጠርሙሱን በአግባቡ እንዲመልስ ሙሉ ስሙን ወረቀት ላይ እየመዘገብኹ ነው፤
‹‹ስም ማን ልበል?››
‹‹ፍርድ ያውቃል!››
‹‹ፍርድ ያውቃል ማን?››
‹‹ፍርድ ያውቃል መንግሥቱ››
‹‹ምን?››
‹‹ፍርድ ያውቃል መንግሥቱ››
‹‹እሺ! ... ዜግነት!››
‹‹ኢትዮጵያዊ!››

https://t.ly/TB5Ld

Addis Admass

14 Nov, 06:10


ጋሽ ኣዳም!]

የራሴ ቀለምና ሀሳብ አለኝ ለሚል ሰው፤ ‹‹እከሌን ትመስላለህ›› መባል ያሳንሳል፡፡ ወይም ጭርስኑ ደስ የሚል ነገር አይደለም፡፡ ነገር ግን ይህ ለምን እንደሚባል ብንመረምረው ሳይሻል አቀርም፡፡ ‹‹እከሌን›› መሆን እፈልጋለሁ እያልን ማደጋችንን ከግምት ስናስገባ፣ ‹‹እከሌን›› ትመስላለህ መባል ለምን የሚሻክር ስሜት ይፈጥርብናል? ተፈጥሮአዊ የሆነው የሀሳብ ጉርምስና ቢሆንም እንዴት ነው መረዳት ያለብን?
ጉዳዩን ቅርብ ለማድረግ የሰዎችን ስም መጠቀም ግድ ስለሚሆንብኝ ለዚህ በቅድሚያ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ ሰው መምሰል ምንድን ነው? ሰዎችስ ለምን በዚህ በኩል ሊያውቁን ይፈልጋሉ? በልባችን ያለው ዝግጅት ይታያቸዋል? ድካማችንን ይገነዘቡታል? እንዲህ ያለውን አስተያየት፤ ፍረጃ እንደሆነ፤ ምን ያህሉ የሚያውቁት ይመስላችኋል? ንክሻ የመሰለን አስተያየታቸው በዚህ መጠን እንደሚያቆስለን ይገባቸዋል? ጥያቄው ይሄ ነው፡፡ ታዲያ እነሱ በዚህ ደረጃ ክብደት ያልሰጡትን አስተያየት እኛ እንዴት እናስተናግደው?
“ነቢይ በአገሩ አይከበርም” የሚለው አነጋገር፣ ‹‹ነቢይ›› የተባለው በእኛ የዕድሜ ክልል ከሆነ የበለጠ ጠንካራ ፈተና የሚገጥመው ይመስለኛል፡፡ የየራሳችንን መንገድ ለመፍጠር የምንደክመው እኛ፤ አባቶቻችንን ንቀን ከአያቶቻችን ጋር የተዛመድን አይደለንም? በህይወት ካሉት ጋር መመሳሰላችንን እንደ ስርቆት አይተን አያቶቻችን ጋር አልተወዳጀንም? ከነሱ ጋር ማበራችን ቅርስ ማስመሰል ወይም አዋቂነት አድርገን አልቆጠርነውም?
ለምሣሌ፦ አንድ ግጥም የሚጽፍ ሰው ቅኔህ እንደ ጸጋዬ ነው ቢባል አይከፋውም፡፡ ይህ እንግዲህ በእኔ ዳሰሳ ያገኘሁትን ነው፡፡ ነገር ግን በእውቀቱን ትመስላለህ ሲባል ወይም እንደ አዳም ነው የምትጽፈው ሲባል ሊከፋው ይጀምራል፡፡ አዳም አንተ ውስጥ ይታየኛል፤ ስንለው ያኮርፈናል፡፡ ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት የተባለበትና የተቀበልንበት መንገድ አልተመረመረም፡፡


ለምሣሌው ሌላ ምሣሌ፤ አንድ ሰው ለሁለት የተለያዩ ሰዎች አንድ ተመሳሳይ ስሜት ወይም ዐይን ካለው፣ ሰዎቹን ሳይሆን እሱን እንመለከታለን፡፡ እምቢኝ ቢል በጉዳዩ ላይ ያለውን ጠንካራ አቋም ማየት እንችላለን፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ለሁለቱም የተለያየ አተያይ ያለው እንደሆነ ግን፤ ጉዳዩ እሱ መሆኑ ይቀርና ሰዎቹ ይሆናሉ፡፡ ወይም ለአንዱ ንቀት ለሌላው ክብር፣ ላንዱ ጥሩ ግምት ለሌላኛው የተጓደለ አመለካከት እንዳለው ልብ ማለት እንችላለን፡፡ ምሣሌው ለተባዩ ብቻ ሳይሆን ለባዩም ጭምር እንደሆነ ሳይዘነጋ፡፡
ምክንያቱ እንዲህ ይመስለኛል፡፡ ጋሽ ጸጋዬና ጋሽ ስብሐት ከአጻጻፍ መንገድ ወጥተው ስም ሆነዋል፡፡ ስለዚህ እንደ ጸጋዬ ትጽፋለህ መባል ግጥምህ ሰንጎ መገል ወይም የወል ቤት ነው እንደማለት ሆኖአል፡፡ ጋሽ ስብሐትንም ቢመስል ተጽዕኖ ወይም ኩረጃ አንለውም፡፡ ይህንን የፈጠረው ጊዜ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ እደግመዋለሁ የሚጫወትብን ጊዜ ነው፡፡ ጊዜ ደግሞ ከድንጋዩ ትህትና በላይ ቅልን ጉልበተኛ ያደርገዋል፡፡ እናም ድንጋዩ እንዲሰበር ይፈርድበታል፡፡
የአጻጻፍ ስልታቸው መለያየት እንዳለ ሆኖ፤ እንደ አዳም ትጽፋለህ መባል ቅር መሰኘቷ ለምን መጣች? ጋሽ ጸጋዬ በእኛ ዕድሜ አለመኖሩና አዳም የኛ ትውልድ አካል ከመሆኑ ጋር የሚያያዝ አይመስላችሁም? እየታየን የምንሰርቅ ስለሚመስለን መባሉ ይሻክረናል፡፡ ይህንን የበለጠ ለመረዳት በየዘመኑ የተነሱ “ኢዝሞችን” ብናስታውስ ሁሉም የአንድ ሰሞን የአስተሳሰብ እንቅስቃሴ እንደሆኑ መረዳት እንችላለን፡፡
ተጨማሪ ያንብቡ
https://t.ly/P6ETb

Addis Admass

14 Nov, 06:07


ደጃዝማች ፀሐዩ - በገሀ ምድር የበቀሉ!

ሀገራችን ኢትዮጵያ ሺህ መልክ ያላት ዝንጉርጉር፣አሳዛኝ ጠባሳዎች ያረፉባት ገላ ያላት ግራ አጋቢ ናት። በተለይ ዘመናዊነት ብለን በምንጠራቸው የዘመን አንጓዎች የዘመርናቸውን መዝሙሮች ከልሰን ስናዳምጥ ደረት ለመድቃት እንጂ አንገት ቀና ለማድረግ የሚነሽጡ ገጾች የሉንም።
ቴዎድሮስ ባሩድ እንጂ ቆሎ ቅሞ አልወደቀም። ባሩድ መቃም የበረከት ማሳያ አይደለም፤የመራራ ምጥ ውሳኔ የነገዎች በር ጭንቅ የሚያመጣው የጥንካሬና የክብር ብይን፤ስለ ነገ ትውልድ ስም የሚከፈል የሕመም ኬላ ነው።
የተወሳሰበ ገጿ የነገ አድማሶቿን በሮች በደደረ ጨለማ በዘጋው ቀን ሁሉ ወደፊት ማየት ሲሳሳና ወደ ኋላ የምናደርጋቸው ሐሰሳዎች ክፉኛ ልባችንን እየቧጠጡ፣የደም እንባ እንድናወርድ ያስገድዱናል።
ይሁንና በዚህ ሁሉ ሕመምና ጨለማ የተጣባው ሰማይ ላይ ብርሃን ሆነው በኮከብነት የተጻፉ ጥቂት ጀግኖች ስላሉን በታሪክ አደባባዮቻችን ልናወሳቸው፣በትዝታ ሸራዎቻችን ላይ ስለን ለትውልድ ልናሻግራቸው የሚገቡ ጥቂት አይደሉም። ዛሬ ዛሬ ለፖለቲካችን እንዲመች አጥብበን ወደየሠፈራችን ድንኳን የወሰድናቸው ባለ ሰፊ ልብ፣ባለ ተከሻ አባቶችን ማሰብና ወደ ተመረጡ ሕልሞቻቸው ማተኮር ያለብን ይመስለኛል።


ሕልማቸው ልማት ሆኖ የሀገር ድንበር ለማስከበርና ልዕናን ለመጠበቅ የተጉ፣ ወደ ኋላ ስናይ ደምቀው ከሚታዩትና ያለ ማስተዋል ካጣናቸው መካከል የንጉሠ ነገሥቱ ባለሟል ደጃዝማች ፀሐዩ ዕንቆሥላሴ አንዱ ናቸው። እኒህ እስከ ጤና ጥበቃ ሚኒስትርነት ደረጃ የደረሱ ባለሥልጣን፣ሀገሪቱ በጠላት እጅ እንዳትወድቅ እስከ ማይጨው ግንባር ሄደው የተዋጉና የሀገራችን ጦር በጠላት ኀይል ሲፈታ ለዐመታት ከሌሎች አርበኞች ጋር በዱር በገደሉ በአርበኝነት የተፋለሙ ናቸው።
የእኚህን ጀግና ታሪክ በተለያዩ መጻሕፍት፣መጽሔቶችና ጋዜጦች ተጠርዘው በጥቂት በጥቂቱ ብናነብብም፤በመጽሐፍ መልክ ተጠርዞ የምናገኘው በዶክተር አማረ ተግባሩ ተጽፎ ነው።ስለ መጽሐፉ ሥነ ጽሑፋዊ ውበትና የአተራረክ ቅደም ተከተል ቅሬታ ቢኖረኝም፣የኒህ ታላቅ ሰው ታሪክ ተሰንዶ መቀመጡን እንደ ትልቅ ውለታ ቆጥሬዋለሁ።

ተጨማሪ ያንብቡ

https://t.ly/1HAwE

Addis Admass

12 Nov, 20:18


የጋዜጠኛ ዜናነህ መኮንን ሥርዓተ-ቀብር ዛሬ ማክሰኞ በእስራኤል ቴል አቪቭ ከተማ ያልሚና ያል ኮን በተባለ ሥፍራ ተፈጸመ። በሥርዓተ ቀብሩ ልጆቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ እና በእስራኤል የሚኖሩ የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ አባላት ተገኝተዋል። ዜናነህ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ኅዳር 1 ቀን 2017 ነበር።
ለረዥም ዓመታት በእስራኤል የኖረው ዜናነህ ከ1968 ጀምሮ በጋዜጠኝነት ሲሰራ ቆይቷል። በኢትዮጵያ ራዲዮ እና ቴሌቭዥን በዜና አንባቢነት ይሠራ ነበር። ኑሮውን በእስራኤል ካደረገ በኋላ በተለያዩ የራዲዮ እና የቴሌቭዥን ጣቢያዎች እንዲሁም በኢንተርኔት የተለያዩ ዝግጅቶች ያቀርብ ነበር።
ከጎርጎሮሳዊው 2013 ጀምሮ የዶይቸ ቬለ የአማርኛው ክፍል የጣቢያ መክፈቻ እና በዝግጅቶች መግቢያነት የሚጠቀምባቸው ማስተዋወቂያዎች አንባቢም ነዉ። የዶቼ ቬለ የአማርኛው ክፍል ኃላፊ ሉድገር ሻዶምስኪ “እኔና ባልደረቦቼ ድንገት በሰማነው ሕልፈቱ ጥልቅ ሀዘን ተሰምቶናል” ብለዋል።
”በኢትዮጵያውያን ትውልድ ውስጥ ድንቅ ከሚባሉት ጋዜጠኞች አንዱ የሆነውን የዜናነህን ሙያዊ አገልግሎትን ለኢትዮጵያውያን እና ለጀርመንም ልዩ ስፍራ ከሚሰጣት ከእስራኤል ለDW ሲያደርገው በቆየው ዘገባ ከተጠቀሙበት መካከል በመሆናችን እራሳችንን እንደ ዕድለኛ እንቆጥረዋለን“ ብለዋል።
ዜናነህ ከጋዜጠኝነቱ ባሻገር “ነጻነት” እና “ከጣራው ስር” የተሰኙ ሁለት ልቦለዶች ለኅትመት አብቅቷል። “በረከተ ራዕይ” የተሰኘ በድምጽ የተቀረጹ የግጥም ስብስቦችም አሉት። ዜናነህ ባለትዳር እና የሶስት ሴቶች ልጆች አባት ነበር።

Addis Admass

12 Nov, 19:58


ፈተናዎችን እየተሻገርን ባሳካናቸው ስኬቶች ሳንረካ የአገልግሎት አሰጣጣችንን ከህዝባችን ፍላጎትና ካስቀምጥነው ስታዳርድ አኳያ፣ ሌብነትና ብልሹ አሰራር ያልተሻገርናቸው መሆናቸውን
አምነን ለመከላከል የዘረጋነዉ አሰራር እንዲሁም ነዋሪው የሰጠንን ጥቆማና አስተያየትን መሰረት በማድረግ የሰራናቸው ስራዎች ፍሬ ማፍራት የጀመሩ ሲሆን አሁንም አፅእኖት ሰጥተን ችግሩን በሚመጥን ደረጃ በዘላቂነት ለማረም የሚያስችል የአመራር ቁመና ለመፍጠር፣ ግልፅነትን እየጨመርን እና ነዋሪውን እያሳተፍን መስራት የሚያስችል አቅጣጫም አስቀምጠናል::
በተጨማሪም በተቋም ግንባታ፣ የሰው ተኮር ስራዎችን ማጠናከር፣ የስራ እድል ፈጠራ፣ የኑሮ ውድነትን በመቀነስ፣ ገቢ አሰባሰብ ማሻሻል፣ የንግድ ስርአቱን ማጠናከር፣ ለነዋሪዎቿ የተመቸች ከተማ መገንባት እንዲሁም የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን በፍጥነት በመጨረስ ወደ አገልግሎት ማስገባት እና የ2ተኛ ዙር ኮሪደር ስራን በጥራት እና በፍጥነት ማጠናቀቅ በቀጣይ በልዩ በትኩረት የምንሰራቸው ስራዎች ናቸው::
አገልግሎት አሰጣጣችንን ይበልጥ ቀልጣፋና ከሌብነትና ብልሹ አሰራር የጸዳ በማድረግ በትጋትና በታማኝነት በማሳተፍ መስራታችንን አሁንም አጠናክረን እንቀጥላለን::
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Addis Admass

12 Nov, 19:57


በዚህ ሩብ ዓመት በየተቋማቱ አቅደን ከፈፀምነዉ አንፃር 86 እጅ ዉጤታማ አፈፃፀም የታየበት ሲሆን ከህዝብ ጋር ተቀራርበን የሰራንበት፣ የአመራር ቅንጅት፣ የስራ ባህላችን መለወጥ እና ከተማችንን የሚመጥን የስማርት ከተማ ግንባታ ስራዎቻችን ስኬት ያገኘንባቸው ናቸው::
በኮሪደር ልማት ምክንያት ለኑሮ ከማይመች ጎስቋላ አካባቢ ያነሳናቸው ነዋሪዎቻችንን ለኑሮ ምቹ የሆነ ንጹህ የመኖሪያ ቤት እና አካባቢ እንዲያገኙ ማድረግ የቻልን ሲሆን ከተማ ብቻ ሳይሆን የሰው ህይወት አብሮ የታደሰበት አፈፃፀም መሆኑንም ገምግመናል::

Addis Admass

12 Nov, 19:56


የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈጻጸማችንን ድክመት እና ጥንካሬዎቻችንን ከነመንስዔዎቻቸው በመለየት ገምግመናል።
የስራ ባህላችን ወጪ ቆጣቢ ፣ጥራትና ባጠረ ጊዜ ውስጥ የሰራናቸው ስራዎች ከተማችንን ለነዋሪው ምቹ ከማድረግ አኳያ ትልቅ ትርጉም ያላቸው ሲሆን አዲስ አበባ የቱሪስት መዳረሻ፣ ዓለም አቀፍ የስበት ማዕከል ለማድረግ እና የሀገራችንን ገፅታ ለመገንባት የሰራናቸው የኮሪደር ልማትና ከተማዋን መልሶ የማደስ ስራዎቻችን ዉጤታማ ሆነዉ ከተማችን በሩብ አመቱ ብቻ 20 የተለያዩ አህጉርና አለምአቀፍ ኮንፍረንሶችን በብቃት ማስተናገድ ችላለች።

Addis Admass

12 Nov, 19:29


በየዓመቱ በሚካሄደው ታላቁ ሩጫ፣ ከቲ-ሸርት ሽያጭና ከስፖንሰር አድራጊዎች ከ2 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ፣ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች ድጋፍ እንደሚውል የጠቆሙት አዘጋጆቹ፤ ዘንድሮ ግን ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ ማሰባሰባቸውን አስታውቀዋል፡፡

ከጎረቤት አገራት በውድድሩ ለመሳተፍ ከሚመጡ ዕውቅ አትሌቶች በተጨማሪ፣ ባለፈው ወር በቺካጎ የዓለም የሴቶች ማራቶን ላይ 2 ሰዓት ከ9 ደቂቃ፣ ከ57 ሰከንድ በመግባት የዓለምን ክብረወሰን የሰበረችው ኬንያዊቷ አትሌት ሩት ቼፔንግኢቲች፣ የክብር እንግዳ ሆና እንደምትገኝ ታውቋል፡፡

አትሌቷ 24ኛውን ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በክብር እንግድነት ለማድመቅ ወደ አዲስ አበባ እንደምትጓዝ የዘገበው የኬንያው “ኔሽን” ጋዜጣ፤ አትሌቷ ከኢትዮጵያውያን አትሌቶች ጋር ለመገናኘት መጓጓቷን ጠቁሟል፡፡

“ኢትዮጵያን የምጎበኘው ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፤ እናም በተለያዩ ውድድሮች ላይ ከተፋለምናቸው አትሌቶች መካከል ጥቂቶቹን ለማግኘት ጓጉቻለሁ፡፡ በሩጫው ለብዙዎች መነሳሳትን የፈጠረው ኃይሌ ገ/ሥላሴንም ስለማገኝ ደስተኛ ነኝ፡፡” ብላለች፤ አትሌቷ ለጋዜጣው፡፡

Addis Admass

12 Nov, 19:29


በዘንድሮ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከ50 ሺ በላይ ሯጮች ይሳተፋሉ

የፊታችን እሁድ በሚካሄደው ሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ውድድር ላይ ከ50 ሺ በላይ ሯጮች እንደሚሳተፉ የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህም ኢትዮጵያ በ10 ኪ.ሜ የጎዳና ሩጫ ላይ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ሰው በማሳተፍ ታሪክ ትሰራለች ተብሏል፡፡

ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ የጎዳና ሩጫ ይሄን ያህል ሰዎች የተሳተፉት በአሜሪካ አትላንታ ብቻ መሆኑ ይታወቃል፡፡

ለዘንድሮው ታላቁ ሩጫ የተለየ ገጽታ የሚሰጠው ሉሲ በተገኘችበት 50ኛ ዓመት ላይ የሚካሄድ በመሆኑ ነው ሲል ለ“ካፒታል” ጋዜጣ የተናገረው አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ፤በዚህም የተነሳ የተሳታፊዎችን ቁጥር ከ45 ሺ ወደ 50 ሺ አሳድገናል ብሏል፡፡

ከ18 የአለም አገራት የሚመጡ ተሳታፊዎች እንደሚካፈሉበት በተነገረለት 24ኛው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ፤ የኡጋንዳና የኬንያ ዕውቅ አትሌቶች እንደሚወዳደሩ ታውቋል፡፡

ዘንድሮ የአሸናፊዎች ሽልማትም ወደ 250 ሺ ብር አድጓል ተብሏል፡፡

Addis Admass

12 Nov, 19:28


የገጣሚ ባንቺዐየሁ አሰፋ የግጥም መጽሐፍ አርብ ይመረቃል

የወጣቷ ገጣሚ ባንቺዐየሁ አሰፋ ዓሊ "ላልዪበላይቱ" የተሰኘ የግጥም መጽሐፍ የፊታችን አርብ ሕዳር 6 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 11 ሰዓት ጀምሮ በብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት (ወመዘክር) አዳራሽ ውስጥ ይመረቃል።

በምረቃ ሥነስርዓቱ ላይ ደራሲ ኃይለመለኮት መዋዕል፣ መምህር የሻው ተሰማ፣ ገጣሚ ዮሐንስ ሞላ፣ገጣሚ አበባ የሺጥላ፣ገጣሚ መንበረማርያም ኃይሉ፣ ገጣሚ ዲበኩሉ ጌታና ሌሎችም ጸሃፍት ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል።

ገጣሚ ባንቺዐየሁ አሰፋ ዓሊ፣ ከገጣሚነቷ ባሻገር፣ በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 በጋዜጠኝነት እየሰራች ትገኛለች።

Addis Admass

12 Nov, 11:19


የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
=====
አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx
ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv

Addis Admass

12 Nov, 11:06


በስፍራው ጥሪ ደርሶቸው የተገኙትን የአደጋ ግዜ ሰራተኞች ቡድን መሪ የነበረችውን ባለሙያ ነፃነት ጡጉማን ከብስራት ጋር ባደረጉት ቆይታ ባለሙያዎቹ የመፀዳጃ ቤቱ ቆይታ አስቸጋሪ የሆነባቸው ሲሆን እግራቸው ተይዘው ወደ መፀዳጃ ቤት ጉድጓድ ተዘቅዝቀው ህፃኗን በህይወት እንድትወጣ ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ህፃኗን ከመፀዳጃ ቤት ለማውጣትም 45 ደቂቃ መፍጀቱን አክለዋል።በሰአቱ ወላጅ እናት እና አባት ራቅ ብለው ይከታተሉ እንደነበር ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን የተናገሩት ነፃነት ህፃኗ በተጠቀለችበት ጨርቅ የማን እንደሆነች ያረጋገጡት የአካባቢው ሰዎች ጥቆማ በመስጠታቸው እናትየው ልትያዝ መቻሉን ገልፀዋል።

በተያዘችበት ወቅት ባለቤቴ ሴት ልጅ ከወለድሽ ከቤት አባርሻለው ስላለኝ ድርጊቱን ልፈፅም ተገድጃለው ስትል ተናግራለች።  ገና የማጠባው ሌላም ልጅ አለኝ ስትል መናገራን ብስራት ሰምቷል። ህፃኗ በመልካም ጤንነት ላይ የምትገኝ ሲሆን ህክምና ተደርጎላት ለአበበች ጎበናም የህፃናት ማሳደጊያ ተሰጥታለች።እናት እና አባትም ፖሊስ ይዞ ምርመራ እያደረገባቸው ይገኛል።

Addis Admass

12 Nov, 11:06


ሴት ልጅ ከወለድሽ ከቤት አባርሻለው ተብያለው ያለችው እናት ገና የወለደቻትን ህፃን መፀዳጃ ቤት ውስጥ ብትጥላትም በህይወት ተረፈች

ድርጊቱ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ጣፎ መጠለያ በተባለ አካባቢ ትላንት ሰኞ ህዳር 2 ከቀኑ 10 ሰአት ከ45 ላይ ተፈፅሟል።

ገና የተወለደች ህፃን ከመፀዳጃ ቤት በህይወት ማውጣታቸውን የአዲስ አበባ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል። ህፃኗን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ከመፀዳጃ ቤት ሲያወጡ የህፃኗ እናት እና አባት እራቅ ብለው ይከታተሉ እንደነበርም ለማወቅ ችለናል ሲሉ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ጉዳዩን ለብስራት ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

አባትየው ሁለት ሚስቶች ያሏቸው ሲሆን ከሁለቱ ሚስቶች 12 ልጅ ወልደዋል። ከአሁኗ ባለቤታቸው 7 ልጆች ያሏቸው ሲሆን ይህችኛዋ ህፃን 8ኛ ልጅ መሆናን እና ባላ ለእናትየው ሴት ልጅ ከወለድሽ ከቤት አባርሻለው  እንዳላት መናገሯን አቶ ንጋቱ ለብስራት ገልፀዋል። በአሁን ወቅት ወላጅ እናት ስትወልድ የወለደቻት ሴት መሆናን ስታይ መፀዳጃ ቤት ውስጥ መጨመሯን ተናግራለች። ከከተተቻት በኃላ የልጅታን ለቅሶ ከመፀዳጃ የሰሙ የአካባቢው ሰዎች ለኮሚሽኑ የአደጋ ባለሙያዎች ጥሪ አድርሰዋል።

Addis Admass

12 Nov, 10:56


የአርባ ምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡-የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴ
የአርባ ምንጭ ዓለም አቀፍ ስታዲየም ግንባታ በሁለት ምዕራፍ ተከፍሎ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የስታዲየሙ ግንባታ የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡
የስታዲየም ግንባታውን ለማጠናቀቅ የገቢ ማሰባሰቢያ መርኀ ግብሮች መያዛቸውን ዛሬ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገልጿል።
የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴው በሰጠው መግለጫ የስታዲየም ግንባታ ሂደቱን አብራርቷል።
በአርባ ምንጭ እየተገነባ የሚገኘው ስታዲየም የሲቪል ስራው አሁን ላይ 40 በመቶ መድረሱ ተነግሯል።
የፊፋ እና የካፍ ደረጃን አሟልቶ እየተገነባ የሚገኘው ስታዲየም 30ሺ ተመልካች የመያዝ አቅም ይኖረዋል ተብሏል።
ወጪውም ሦስት ቢሊየን ብር እንደሚሆን ተገልጿል።
የስታዲየም ግንባታው በፍጥነት እንዲጠናቀቅ የገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴው ከእሺ ሚዲያ ጋር አብሮ ለመስራት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።
ኢትዮጵያ በ2029 የአፍሪካ ዋንጫ የማስተናገድ ዕድል ከተሰጣት ስታዲየሙን ለውድድሩ የማድረስ እቅድ እንዳለ የገለጸው ኮሚቴው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየተከታተለው እንደሚገኝ ገልጿል።
ከገቢ ማሰባሰብ ጋር በተያያዘ ዘጠኝ መንገዶችን መለየታቸውም ተነግሯል።
ጨረታ ፣ ኮንሰርት ማዘጋጀት ፣ የሩጫ ውድድር ፣ የእግር ኳስ ጨዋታ እና ሌሎች መርሃ ግብሮችም ይዘጋጃሉ ተብሏል።
AMN

Addis Admass

12 Nov, 07:29


የዩኒቨርሲቲ መምህራን የቤት መሥሪያ ቦታና
ነጻ ህክምና እንዲያገኙ ተጠየቀ


የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር፣ የዩኒቨርሲቲ መምህራን የመኖሪያ ቤት መሥሪያ ቦታና ነጻ ህክምና እንዲያገኙ ለመንግሥት ጥያቄ አቀረበ፡፡

ማህበሩ ለትምህርት ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ፣ እንደሌሎች የመንግሥት ሠራተኞች ሁሉ፣ መምህራንም የበረሃና የውርጭ አበል እንዲከፈላቸውም ጠይቋል፡፡

ዩኒቨርሲቲዎች በሚገኙባቸው ክልሎች ሁሉ መምህራኑ የአካባቢውን ማህበረሰብ እያገለገሉ ቢሆኑም፣ “ዩኒቨርሲቲዎች የፌደራል ተቋም ናቸው” በሚል የቤት መሥሪያ ቦታ ሳያገኙ ቀርተዋል ብሏል - ማህበሩ፡፡

መምህራኑ በሚያስተምሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች በሚገኙ የጤና ተቋማት እየከፈሉ እንደሚታከሙ የጠቀሰው ማህበሩ፤ ይህም የሥራ ተነሳሽነታቸውን እንደቀነሰው በመግለጽ፣ ከእነ ቤተሰባቸው ነጻ ህክምና እንዲያገኙ ለት/ሚኒስቴር በጻፈው ደብዳቤ ጠይቋል፡፡

Addis Admass

12 Nov, 06:15


https://t.ly/nCrGh

Addis Admass

11 Nov, 20:47


https://t.ly/g1s5F

Addis Admass

11 Nov, 20:02


“ቁና - እህል ጠላ ጨረስን እባካችሁ፤ ማጥለያ ስጡን”

አንድ አባ ዳካ የሚባሉ በሠፈር ባገሩ በጨዋታና በነገር አዋቂነታቸው የታወቁ አዛውንት በየጊዜው በየዕድሩ፣ በየሰንበቴውና በየድግሱ ሁሉ እየተገኙ በሚያጋጥማቸው ነገር ላይ ይተርባሉ፣ ወግ ያወጋሉ፣ ቀልድ ይቀልዳሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ሰው አባባላቸውን እየጠቀሰ፤ “አባ ዳካ እንዲህ አሉ” እያለ ይተርታል፡፡ አለቃ ገብረ- ሃና እንዲህ አሉ፡፡ ካሳ ደበሉ እንዲህ አሉ፤ እንደሚባለው መሆኑ ነው፡፡
አባ ዳካ፣ አንድ ቀን ከአንድ ሹም ጋር ተጣልተው በብዙ ጅራፍ ተገርፈው ሲመጡ ወዳጃቸው የሆነ ሰው ያገኛቸውና “ምን አርገው ነው እንዲህ የተገረፉት አባ ዳካ?” ሲል ጠየቃቸው፡፡
አባ ዳካ፣ “ያየሁትን ተናግሬ” ይላሉ፡፡
“ምን አይተው፣ ምን ተናገሩ?” ብሎ ይጠይቃቸዋል፡፡
“ትላንትና ወንዝ ወርጄ ውሃ ቀጂዎቹ እወንዙ ዳር ሆነው በብዛት ውሃ ይቀዳሉ፡፡ ይሄኔ አንድ ሹም ከሚስቱ ጋር ይመጣል፡፡ ከዚያም ሚስቱ ከሌሎቹ ውሃ-ቀጂዎች እኩል መቅዳቷ የውርደት ይመስለውና፣ በሰላም ውሃ እየቀዱ ያሉትን ሴቶች፣ “አንቺ መጀመሪያ፣ ቀጥሎ አንቺ፣ ቀጥሎ አንተ” ማለት ጀመረ፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

https://t.ly/-gcKL

Addis Admass

08 Nov, 21:07


እስራኤላዊያን የእግር ኳስ ደጋፊዎች ጥቃት ደረሰባቸው

በሆላንድ እስራኤላውያንን ኢላማ ባደረገ ጥቃት፣ ቢያንስ አምስት ሰዎች ተጎድተው ሆስፒታል መግባታቸው ተነገረ፡፡ ጥቃቱ የተከሰተው የእስራኤሉ የማካቢ ቴላቪቭ ቡድን በአያክስ አምስተርዳም 5 ለ 0 ከተሸነፈበት ጨዋታ በኋላ ነው። ደጋፊዎች ከስታዲየም ከወጡ በኋላ ግጭት መቀስቀሱም ተገልጿል።
በጥቃቱ የተጠረጠሩ 62 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአምስተርዳም ከተማ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ የእስራኤሉ ማካቢ እግር ኳስ ቡድን ከሆላንዱ አያክስ ጋር ባደረጉት ጨዋታ፣ ለድጋፍ የሄዱ እስራኤላውያን በአምስተርዳም ከሚገኙ ፍልስጤማውያን ጋር ግጭት ውስጥ ገብተዋል።

የእስራኤል መንግስት የዜጎቹን ህይወት ለመታደግ በፍጥነት ሁለት የህይወት አድን አውሮፕላኖችን ወደ ሆላንድ መላኩ ተዘግቧል፡፡

Addis Admass

08 Nov, 21:05


የ20 ሚሊዮን ብር ሎተሪ አሸናፊው ገንዘባቸውን ተረከቡ


የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት፣ በእንቁጣጣሽ ሎተሪ 20 ሚሊዮን ብር እድለኛ ለሆኑት አቶ አስረሳኸኝ ጌታቸው፣ ገንዘቡን በዛሬው እለት አስረክቧል።

በኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርስቲ በመምህርነት የሚያገለግሉት ግለሰቡ፤ ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ ጉዞ ለማድረግ በተገኙበት ቃሊቲ መናኸሪያ ውስጥ የቆረጡት የሎተሪ ትኬት የ20 ሚሊዮን ብር እድለኛ አድርጓቸዋል።

በተለያዩ ጊዜያት የሚወጡ ሎተሪዎችን የመቁረጥ ልምድ እንዳላቸው የተናገሩት ዕድለኛው ግለሰብ፤ ይህን ግን ሻጩ አስጨንቆኝ እንጂ ለመቁረጥ አስቤ አልነበረም ብለዋል፡፡ ዕድለኛው ግለሰብ ሳያስቡት ገፋፍቶ ላስቆረጣቸው ሎተሪ ሻጭም ምስጋና አቅርበዋል።

አቶ አስረሳኸኝ ጌታቸው፣ ያገኙትን ገንዘብ የተለያዩ ቁም ነገር ስራዎች ላይ ለማዋል ማቀዳቸውን ተናግረው፣ ሁሉም ሰው ተስፋ ሳይቆርጥ ዕድሉን እንዲሞክርም መክረዋል።

Addis Admass

08 Nov, 20:49


ውድ አንባቢያን
ሳምንታዊ የቅዳሜ ጋዜጣችሁን አዲስ አድማስን፣ በእነዚህ
የመዲናችን መፃሕፍት መደብሮች ውስጥ እንደምታገኙት
ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
• ጃፋር መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ)
• ክብሩ መፃሕፍት መደብር (ጥቁር አንበሳ፣ ትራኮን ህንጻ)
• እነሆ መፃሕፍት መደብር (አራት ኪሎ)
• ኢዞጵ መፃሕፍት መደብር (አቡነ ጴጥሮስ)
• አምደ መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ) አዲስ አድማስ የእርስዎና ቤተሰብዎ

Addis Admass

08 Nov, 20:13


ፍራንኮ ቫሉታ ሙሉ በሙሉ ተከለከለ

የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና ለጉምሩክ ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤ፤ ፍራንኮ ቫሉታ ከዛሬ ጥቅምት 29 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ መከልከሉን አስታውቋል፡፡

የብር የመግዛት አቅም በገበያው እንዲወሰን ከተደረገ በኋላ ለተወሰነ ጊዜ የነዳጅ ተሽከርካሪዎችንና የፀጥታ ተቋማት መሳሪያዎችን ሳይጨምር ሌሎች ምርቶችን በፍራንኮ ቫሉታ ወደ ሀገር ማስገባት ተፈቅዶ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ይሁንና ከሳምንት በፊት ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በፓርላማ ተገኝተው በሰጡት ማብራሪያ፤ የተፈቀደው ፍራንኮ ቫሉታ ሀብት ከሀገር እንዲሸሽ ምክንያት እየሆነ በመሆኑ ሊታገድ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥተው ነበር፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ዛሬ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና ለጉምሩክ ኮሚሽን በፃፈው ደብዳቤም፤ ከዚህ ቀደም በፍራንኮ ቫሉታ ሸቀጦችን ከውጪ ያዘዙ ካሉ ከዛሬ ጀምሮ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ግዢ የተፈፀመባቸው ህጋዊ ሰነዶችን ለጉምሩክ ኮሚሽን በማቅረብ ተቀባይነት አግኝተው የንግድ ሸቀጦቹ ወደ ሀገር ውስጥ እንዲገቡ ይደረጋል፤ ብሏል፡፡

Addis Admass

08 Nov, 20:08


የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
=====
አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx
ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv
🟠 በማለዳ ይጠብቁን!! 🟠

Addis Admass

08 Nov, 19:53


ዶ/ር ተሻለ አሰፋ ነገ ቅዳሜ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ አራት ኪሎ "ንቃ " ቡና ከብዙ ቤተሰቦች ጋር ቀጠሮ ይዟል! እናንተስ

በዶ/ር ተሻለ አሰፋ የተፃፈው

"የተውኔት ዝግጅት መሰረታዊያን " የተሰኝውን መፅሐፍ ገዝተው ለማስፈረምና ከተሼ ጋር ቡና እየጠጡ ለመጨዋወት በርካታ የኪነጥበብ ባለሙያዎች ጋዜጠኞች የእርሱ ተማሪዎች ወዳጆቹ ነገ ቅዳሜ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋት 3:00-5:00 ሰዓት "ንቃ ቡና" ቀጠሮ ይዘዋል!!

በዚህ የመፅሐፍ ግዢ ዘመቻ ላይ ተሳትፋችሁ ገንዘቡን በአካውንቱ ያስገባችሁ ወዳጆች ነገ በተጠቀሰው ሰዓት ተገኝታችሁ የገዛችሁትን መፅሐፍ ዶ/ር ተሻለ አሰፋ በስማችሁ ፈርሞበት በክብር ይሰጣችኃል:: እናንተስ?
"የተውኔት ዝግጅት መሰረታዊያን " ን ያልገዛችኹ፣ ገዝታችኹ ተሼ እንዲፈርምላችኹ የምትፈልጉ ነገ ጎራ በሉ!!

የቅድሚያ ግዢ ዘመቻ ላይ ለመሳተፍና መፅሐፉን
ከደራሲው ከዶ/ር ተሻለ ለመግዛት የምትፈልጉ ሁሉ ከታች ባለው አካውንት ከአንድ መፅሐፍ ጅምሮ መግዛት ትችላላችሁ:: እርሱም በስማችሁ ፈርሞ ይሰጣችኃል:: የአንዱ መፅሐፉ ዋጋ :- 560 ብር ነው::

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:
የተሻለ አሰፋ የባንክ ሂሳብ ቁጥር:-
1000024912659
ስልክ ቁጥር:-
+251 91 201 6775
ደውለው ተሻለን ያናግሩ::

አድራሻ:- "ንቃ ቡና"
ከአራት ኪሎ ወደ ፒያሳ በሚወስደው መንገድ፣
ከአራዳ ክፍለ ከተማ አጠገብ፤ አንግላ በርገር የሚገኝበት አንደኛ ፎቅ።

Addis Admass

08 Nov, 19:40


በትራምፕ ማሸነፍ ጭንቀትና ድባቴ
ውስጥ የገቡ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች!!

• ለትራምፕ የሥልጣን ዘመን በሥነልቦና እንዲዘጋጁ እየታገዙ ነው


ባለፈው ረቡዕ የዶናልድ ትራምፕን በከፍተኛ ድምጽ ማሸነፍ ተከትሎ፣ ሃርቫርድና ፕሪንስተንን በመሳሰሉ ዩኒቨርስቲዎች በርካታ ክፍሎች (ኮርሶች) ተሰርዘው መዋላቸው ተዘግቧል፡፡ በደስታና በፌሽታ እንዳይመስላችሁ፡፡ በሃዘን፣ በስሜት መናወጥ፣ በጭንቀትና በድባቴ ነው ተብሏል፡፡

በሃገረ አሜሪካ እኒህ ዩኒቨርሲቲዎች፣ የግራ አክራሪ ልሂቃን (Radical leftist ይሏቸዋል) መፈልፈያ ከሆኑ ከራርመዋል፡፡ እናም ረቡዕ ዕለት የትራምፕ ታሪካዊ የምርጫ ድል ከተሰማ በኋላ፣ ዩኒቨርስቲዎቹ፣ ተማሪዎቻቸው ከምርጫ ውጤቱ “ያገግሙ” ዘንድ ትምህርት ዘግተው ውለዋል፡፡

ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች በተጨማሪም፣ ኹነቱን በጥንቃቄ ማስተናገዳቸውም ነው የተነገረው - የካማላ ደጋፊ የሆኑ ተማሪዎች፣ ለትራምፕ ሁለተኛ የሥልጣን ዘመን በሥነልቦና እንዲዘጋጁ በቂ ጊዜና ቦታ በመስጠት፡፡

ተማሪዎቹን “የድህረ-ምርጫ ሃዘንና ድባቴ” ውስጥ የከተታቸው ምክትል ፕሬዚዳንቷ ካማላ ሃሪስ በምርጫው የመሪነቱን ቦታ ይወስዳሉ ብለው ሲጠብቁ በሪፐብሊካኑ እጩ ዶናልድ ትራምፕ በዝረራ መሸነፋቸው ነው ተብሏል፡፡

በሃርቫርድ ተማሪዎች የሚዘጋጀው “ዘ ሃርቫርድ ክሪምሶን” ጋዜጣ እንደዘገበው፤ ባለፈው ረቡዕ በዩኒቨርሲቲው የሚሰጡ አንዳንድ ኮርሶች ሲሰረዙ፣ በክፍል ውስጥ መገኘት የግድ አልነበረም፡፡ የቤት ሥራ (Assignment) የማስረከቢያ ቀናትም መራዘማቸው ተዘግቧል፡፡

“በሃርቫርድ ያለው እንደመሆኔ፣ የሃሪስ ደጋፊ በሆኑ ብዙ ሰዎች ተከብቤ ነበር፤ ስለዚህ በአዕምሮዬ ቀድሞ የተወሰነ ምርጫ ነበር” ያለችው ሳማንታ ሆልዝ፤ “ለእኔ ትንሽ አስደንጋጭ ነበር” ብላለች፡፡ (የምርጫው ውጤት ወይም የትራምፕ ማሸነፍ ማለቷ ነው)

የማታ ማታ፣ የሃርቫርድ ኮሌጅ ዲሞክራቶች፣ ካማላ ሃሪስ ሽንፈት ቢገጥማቸውም፣ ድጋፋቸውን ሰጥተዋቸዋል፡፡ ባወጡት መግለጫም፤ ”የሃርቫርድ ኮሌጅ ዲሞክራቶች፣ ለምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ሃሪስ አመራርና ለአገሪቱ መጪ ዘመን ላሳዩት ራዕይ ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡” ብለዋል፡፡ “በደስታ፣ በማሕበረሰብና በታላቅ ህዝብ አቅም ላይ ያማከለ ዘመቻ በመደገፋችን ኩራት ይሰማናል፡፡” ሲሉም አክለዋል፤ በመግለጫቸው፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ፣ ፕሪንስተን ዩኒቨርሲቲም ባለፈው ረቡዕ ቢያንስ ሁለት የትምህርት ክፍሎችን መሰረዙን “ናሽናል ሪቪው” ዘግቧል፡፡ በተጨማሪም በነጋታው ሐሙስ በትምህርት መጀመሪያ ላይ፣ ተማሪዎች፣ በክፍል ውስጥ ለመሳተፍ በሥነልቦና ዝግጁ ካልሆኑ፣ መሃል ላይ አቋርጠው መውጣት እንደሚችሉ ተነግሯቸው ነበር ተብሏል፡፡ (ለዚህ ሁሉ ሰበቡ እንግዲህ የካማላ መሸነፍ ወይም የትራምፕ ማሸነፍ ነው)

ከምርጫው ውጤት ጋር ተያይዞ የተፈጠረውን የተማሪዎች ሃዘን፣ ጭንቀትና ድባቴ ለመቅረፍ፣ በፕሪንስተን የሚገኝ የዩኒቨርሲቲ የጤና አገልግሎት፣“ የድህረ-ምርጫ የመደማመጥ መድረኮችን” አዘጋጅቶ ነበር - ባለፈው ረቡዕ፡፡ ሌሎች በርካታ የማሕበረሰብ “የድህረ-ምርጫ ውይይቶች” መዘጋጀታቸውም ተነግሯል፡፡

Addis Admass

08 Nov, 19:30


በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር
ወረዳ ከነገ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ አስታወቀ
የክልሉ ሠላምና ፀጥታ ቢሮ በወቅታዊ የፀጥታ ሁኔታ ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ሠላምና ፀጥታ ቢሮ
ኃላፊ አቶ ተመስገን ካሳ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ ስር ያሉ ቆሴ ከተማ፣ ባረዋ እና ደያስ ቀበሌያት በ2014 ዓ.ም የፀጥታ ችግር መከሰቱን አስታውሰዋል።
በከተማውና ቀበሌያቱ የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር ለመፍታት የክልሉ መንግሥት ከቀበሌያቱ ህብረተሰብ ጋር ውይይት ማድረጉን ጠቅሰው በውይይቱ የመልካም አስተዳደርና የፖለቲካ ጥያቄዎች መኖራቸውን መለየት መቻሉን ገልፀዋል።
ህብረተሰቡ በውይይቱ ወቅት ያነሳቸው ጥያቄዎች የክልሉ መንግስት አጥንቶ ምላሽ የሚጥባቸውን መሆኑን ያነሱት አቶ ተመስገን ከዚህ አቅጣጫ በታቃራኒው በአከባቢው ህዝብና በመንግሥት መካከል መተማመን እንዳይፈጠር የሚሰሩ ኃይሎች ለህግ እንቀርቡ የሚደረግ መሆኑን ገልፀዋል።
የህብረተሰቡን ጥያቄ ሽፋን በማድረግ የግል ጥቅም ፈላጊዎች በአካባቢው አለመረጋጋት እንዲፈጠር የሚሰሩ አካላት ላይ የህግ የበላይነትን ለማስከርና የህብረተሰቡ ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አቶ ተመስገን ተናግርዋል።
በመሆኑም በጉራጌ ዞን እኖር ኤነር መገር ወረዳ ስር ያሉ ቆሴ ከተማ፣ ባረዋ እና ደያስ ቀበሌያት ከነገ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም ጀምሮ የእንቅስቃሴ ሰዓት ገደብ መጣሉን ገልፀዋል።
በዚህ መሠረት በዞኑ ከላይ በተጠቀሱ ቀበሌያት ከነገ ጥቅምት 30/2017 ከሌሊቱ 12 እስከ ምሽት 12 ሰዓት ብቻ እንቅስቀሴ የሚደረግ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።
ከምሽቱ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሌሊቱ 12 ሰዓት ድረስ የሁለት እግር ሞተር ሳይክል፣ የሶስት እግር ባጃጅና ሌሎች ተሽከርካሪዎች አንዲሁም የሲቪል ግለሰቦች እንቅስቃሴ የማይኖር መሆኑን ጠቅሰው፣ የፀጥታ መኪና ስለመሆኑ ያልተረጋገጠ ማንኛዉም ተሽከርካሪ በተጠቀሱት ቀበሌያት መንቀሳቀስ እንደማይችል የገለፁት ኃላፊው በፌዴራል ዋና መንገድ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎችን ገደቡ አያካትትም ብለዋል።
የሰዓት ገደብ በተጣላባቸው ሰዓታት የጤና ተቋማት አገልግሎት የማይቆም መሆኑን ኃላፊው ገልፀዋል።
በ2014 ዓ.ም በቀበሌያቱ ህዝብ ንብረት መውደምና በዜጎች መፈናቀል የተሳተፉና በአካባቢው አሁናዊ መረጋጋት እንዳይኖር የሚሰሩ አካላትን ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ለህግ እንዲቀርቡ በማድረግ ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ሲሉም አቶ ተመስገን ጥሪ አቅርበዋል።
Central Ethiopia Regional Government Communication Affairs bureau

Addis Admass

08 Nov, 18:50


10ኛው የአፍሪካ ጨርቃ ጨርቅ እና ፋሽን ሳምንት (ASFW) ተከፈተ፡፡
ከ30 ሀገራት የተውጣጡ የጨርቃ ጨርቅ እና ቆዳ ኢንዱስትሪዎች በአፍሪካ ሶርሲንግ ፋሽን ሳምንት (ASFW) ከዛሬ ጥቅምት 29 እስከ ህዳር 2 /2017 ዓ.ም እንደሚካሄድ ተገልጿል ፡፡

የፋሽን ሳምንቱ የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚንስቲር አቶ መላኩ አለበል እና የቱሪዝም ሚኒስቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሳላማዊት ካሳ እና  ሌሎች በርካታ እንግዶች በተገኙበት ተከፍቷል፡፡

ሚኒስትሩ አቶ መላኩ እንዳሉት አፍሪካ በተፈጥሮ ሃብት የበለፀገች እና ትልቅ አምራች ሃይል ያለባት እንደመሆኗ አሁን ያለችበት ድህነት የማይገባት ነው ብለዋል ፡፡

ሚኒስትሩ አክለውም አፍሪካን ለመቀየር አመራር እና ተቋምን መገንባት ይገባናልም ብለዋል፡፡

ከሁለት አመት በፊት በጀመር ነው ኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በጨርቃ ጨርቅ፣ በቆዳ ዘርፍ እና በኢንዱስትሪ ውጤቶች ተስፋ ሰጪ ለውጥ እየተመዘገበ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዝግጅቱ ከ60 በላይ ሀገራት የሚመጡ ከ7 ሺህ በላይ የንግድ ትስስሩን የሚያሳልጡ ተሳታፊዎች ተገኝተዋል ።

በጨርቃጨርቅና ቆዳ ፋሽን  ሳምንቱ ልምድና ተሞክሮ የሚቀሰምባቸው  የዘርፉን ችግሮች መፍታት ላይ ያተኮሩ ኮንፈረንሶችና የፓናል ውይይቶች እንደሚኖሩም ይጠበቃል ።

የአፍሪካ ሶርሲንግና ፋሽን ሳምንት በ10 አመት ቆይታው ከ50 ሺህ በላይ አዳዲስ ሥራዎችን መፍጠር የቻለ መሆኑም ተገልጿል።

Addis Admass

08 Nov, 09:26


የአስር አመት እድገት እና ልቀት በASFW - Africa Sourcing and Fashion Week ከጥቅምት 29 እስከ ህዳር 2 ቀን 2024 በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል 10ኛ አመት እናከብራለን። የንግድ እድሎችን እና ትብብርን ለሚፈልጉ ከ7000 በላይ አለምአቀፍ የንግድ ኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ጋር ዝግጁ ሆነን እንጠብቆዋታለን።
ይህ የእርስዎን የምርት ስምዎን በተለዋዋጭ ማህበረሰብ መካከል ለማሳየት እድሉ ነው።

Addis Admass

08 Nov, 09:22


ለክቡራን የኪነጥበብ ቤተሰቦች ዛሬ አርብ 11፡30 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር የሚቀርበው ‹‹ የሕይወት ታሪክ›› የተሰኘ አዲስ ቴአትር መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡
Ethiopian National Theatre

Addis Admass

08 Nov, 09:17


የኢትዮጵያ እና ሩሲያ የትምህርት ተቋት በትብብር ለመስራት ተስማሙ

የኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስቴር እና የሩሲያ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር፤ በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በትብብር ለመስራት የሚያስችላቸውን የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል።

እኩልነት፣ የጋራ ተጠቃሚነትና ውጤታማነት መርህ ላይ የተመሰረተ ነው የተባለው ይህ ስምምነት፤ ሁለቱ ሀገራት በከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸው ነው ተብሏል።

የኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ በዚህ ወቅት፤ ሩሲያ የሰው ሃይል በማብቃት ዙርያ ድጋፏን አጠናክራ እንድትቀጥል ጠይቀዋል። ስምምነቱን ወደ ተግባር ለማስገባት፤ በሁለቱም ሀገራት በኩል የቴክኒክ ቡድን እንደሚቋቋም፤ የኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው መረጃ አስታውቋል፡፡

Addis Admass

08 Nov, 09:10


(49ኛው ዙር የዐውደ ፋጎስ የውይይት ክበብ)

በፍልስፍና መምህሯ በኤደን አባተ ይቀርባል!
ቀን :-እሁድ 01/03/2017 ዓ.ም
ሰዓት:- ከቀኑ 8:00
ቦታ :-የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ መዛግብትና ቤተ መጻሕፍት (ወመዘክር)

Addis Admass

08 Nov, 08:43


ከሚመረቱ የፋይዘር (Pfizer) ሳንባ ምች ክትባቶች ውስጥ ከ50 በመቶ በላይ የሚሆኑት ከGavi ጋር በመተባበር ዝቅተኛ እና ዝቅ ያለ መካከለኛ ገቢ ባላቸው አገሮች ውስጥ ተደራሽነትን ለመደገፍ እንደሚቀርቡ ተጠቅሷል። በተጨማሪም፣ እ.ኤ.አ. ከ2020 ጀምሮ፣ Pfizer (ፋይዘር) የአገሪቱን የክትባት ጥረቶች ለመደገፍ ከ40 ሚሊዮን በላይ የኒሞንያ ክትባቶችን “አቅርቧል” ተብሏል።


የክትባት ትብብር የሆነው Gavi ዓለም አቀፍ የጤና ድርጅቶችን፣ የክትባት ኢንዱስትሪውን እና ሌሎች ዘርፎችን የሚያሰባስብ የህዝብ እና የግል አጋርነት እንደሆነ ተወስቷል። ፋይዘር (Pfizer) ደግሞ ለ175 ዓመታት በሕክምና እና በመድሃኒት ቅመማዎች ላይ ሲሰራ ስለመቆየቱ ተጠቁሟል።

Addis Admass

08 Nov, 08:43


ፋይዘር አንድ ቢሊዮንኛ ክትባቶችን ለኢትዮጵያ አበረከተ

ፋይዘር የመድሃኒት አምራች ኩባንያ Gavi በተሰኘው ጥምረት አማካይነት አንድ ቢሊዮንኛ የሳንባ ምች ክትባቶችን ለኢትዮጵያ ማበርከቱ ተነገረ። ኩባንያው እ.ኤ.አ. 2020 ጀምሮ ለኢትዮጵያ የሳንባ ምች ክትባት ሲያቀርብ መቆየቱ ተገልጿል።

የGavi ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ሳኒያ ኒሽታር እንዳመለከቱት፣ Gavi እ.ኤ.አ. ከ2000 ጀምሮ ከአንድ ቢሊዮን በላይ ሕፃናትን እንዲከተቡ የቻለበት የስኬት ምክንያት በልዩ ሁኔታ ብዙ ባለድርሻ አካላትን የሚያካትት ሞዴል በመከተሉ መሆኑን አስታውቀው፣ “የክትባት አምራቾች በዚህ [የGavi] አጋርነት ውስጥ ወሳኝ ሚና የሚጫወቱ ሲሆን፣ ይህም ለክትባቶች አቅርቦት ጤናማና ተመጣጣኝ ገበያዎችን ለመፍጠር፣ ብሎም አዳዲስ የፈጠራ መፍትሔዎችን ለማቅረብ ይረዳናል። ከPfizer ጋር በመሆን ከዚህ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ በመድረሳችን ኩራት ይሰማናል። እንዲሁም ወደፊት የሚኖረንን ውጤታማ ትብብር በጉጉት እንጠብቃለን።” ብለዋል።

የፋይዘር (Pfizer) የአዳዲስ ገበያዎች ፕሬዝዳንት የሆኑት ኒክ ላጉኖቪች "በዓለም ዙሪያ ያሉ ሕጻናት ረዘም ያለ እና ጤናማ ሕይወት የመኖር ዕድል እንዲኖራቸው ለማድረግ ከGavi ጋር ባደረግነው ቀጣይነት ያለው ትብብር እንዲህ ያለ አስገራሚ ምዕራፍ ላይ በመድረሳችን በጣም ደስተኞች ነን። ግን ስራችን እዚህ ላይ አያበቃም" ሲሉ ተናግረዋል። አያይዘውም፣ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸው 45 አገሮች ውስጥ ከዓለም አቀፍ የጤና ድርጅቶች፣ ከመንግስታት እና ከሌሎች ወገኖች ጋር በመተባበር ቀጣይነት ያለው፣ ትርፍን መሰረት ያላደረገ የመድሃኒት እና ክትባቶች ተደራሽነት እንዲኖር እንዲሁም በጣም ተጋላጭ ለሆኑ አካላት የጤና እኩልነት ክፍተትን ለማጥበብ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

Addis Admass

08 Nov, 08:33


ነገ ቅዳሜ ጥቅምት 30  2017 ዓ.ም ከቀኑ 8:00 ጀምሮ ምኒልክ ሆስፒታል አካባቢ በሚገኘው "FSS" አዳራሽ ውስጥ ይካሄዳል።

የፕሮግራሙ አዘጋጅና አቅራቢ ደራሲ እንዳለጌታ ከበደ ነው።

Addis Admass

08 Nov, 07:48


መንታ ፍቅር:: አዲስ አስገራሚ: ግራ እያገባን እየሳቅን ዋሽንግተን እና እዲስ አበባ የምንመላለስበት ፊልም:: አርብ ፡ ጥቅምት 29:በ 8: በ10: በ1 ሰዓት:: ቅዳሜና እሁድ በ8: 10: 12 ሰአት ተጋብዘዋልና ይምጡ !

Addis Admass

05 Nov, 20:53


የ17 ወራት ደሞዝ አልተከፈለንም ያሉ በትግራይ የሚገኙ መምህራን በፌደራሉ መንግስት እና በክልሉ አስተዳደር ላይ ክስ መሰረቱ። የትግራይ መምህራን ማሕበር ያልተከፈለው የአስተማሪዎች ደሞዝ እንዲለቀቅ እስከ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ድረስ በመቅረብ መፍትሔ እንዲሰጠው ተደጋጋሚ ጥረት ማቅረቡ የሚገልፅ ሲሆን፥ ይህ ምላሽ ባለማግኘቱ ጉዳዩ ለሕግ ማቅረቡ አስታውቋል።
በትግራይ የሚገኙ አጠቃላይ የክልሉ መንግስት ሰራተኞች በተለይም ደግሞ በክልሉ መንግስት የተቀጠሩ አስተማሪዎች፥ የፌደራል መንግስቱ እና የትግራይ ሐይሎች ጦርነት ላይ በነበሩበት ወቅት የሰሩበት ደሞዝ እንዲከፈላቸው በተደጋጋሚ ጥያቄ ሲያቀርቡ፣ በአንዳንድ አካባቢዎች የስራ ማቆም አድማ ሲያደርጉ ቆይተዋል።

የ2014 ዓመተምህረት ሙሉ ዓመት፣ የ2015 ዓመተምህረት ደግሞ አምስት ወራት፥ በአጠቃላይየ17 ወራት ደሞዝ አልተከፈለንም የሚሉ እነዚህ በትግራይ የሚገኙ መምህራን፥ ቅሬታቸው ለክልሉ አስተዳደር እና የፌደራል መንግስት በተደጋጋሚ ቢያቀርቡም በቅርቡ ይከፈላል ተብሎ ከተገባ ቃል ውጭ እስካሁን ይገባናል ያሉት ክፍያው አለመፈፀሙ ይናገራሉ። በተደጋጋሚ በሚያወጣቸው መግለጫዎች የመምህራኑ ጥያቄ መፍትሔ እንዲያገኝ ጥሪ ሲያቀርብ የቆየው የትግራይ መምህራን ማሕበር እንዳስታወቀው፥ የክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር እና የፌደራሉ መንግስት እስካሁን ምላሽ ባለመስጠታቸው ጉዳዩ ለሕግ ማቅረቡ አስታውቋል። የትግራይ መምህራን ማሕበር ምክትል ፕሬዝደንት መምህርት ንግስቲ ጋረድ ለዶቼቬለ እንዳሉት፥ ያልተከፈለው የትግራይ መምህራን ጥያቄ ጉዳይ ይዘን እስከ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ድረስ ቅሬታ ማቅረባቸው ይሁንና እስካሁን መፍትሔ ስላልተሰጣቸው በፌደራሉ መንግስት እና በትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ላይ ማሕበራቸው ክስ መመስረቱ ገልፀውልናል።
የትግራይ መምህራን ማሕበርበትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር እና የፌደራሉ መንግስት የመሰረተው ክስ በትግራይ ከፍተኛ ፍርድቤት እየታየ መሆኑ የገለፁልን የመምህራን ማሕበሩ ጠበቃ ዳዊት ገብረሚካኤል በበኩላቸው፥ የትግራይ ክልል እና የፌደራሉ መንግስት የፋይናንስ መስርያቤቶች ጨምሮ ሌሎች ተቋማት መክሰሳቸው ገልፀውልናል። ጠበቃ ዳዊት የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር፣ የትግራይ ትምህርት ቢሮ፣ የትግራይ ፋይናንስ ቢሮ እና የፌደራሉ መንግስት ፋይናንስ ሚኒስቴር በዚሁ የመምህራን ጉዳይ ተከሳሽ የመንግስት ተቋማት መሆናቸው ለዶቼቬለ ገልፀዋል።

የትግራይ መምህራን ማሕበር እንደሚለው የ2014 ዓመተምህረት የ12 ወራት ደሞዝ ከፌደራል መንግስቱ፣ የ2015 ዓመተምህረት የ5 ወራት ደሞዝ ደግሞ ከትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር እንዲከፈላቸው እንደሚጠብቁ ይገልፃል። መምህርት ንግስቲ ጋረድ "ሕግ ካለ የአስተማሪው ደሞዝ ይከፈላል ብለን እናምናለን" ሲሉ ጨምረው ገልፀዋል። በዚሁ የትግራይ መምህራን ጥያቄ እና ያቀረቡት ክስ ዙርያ ከክልሉ አስተዳደር እና የፌደራል መንግስቱ አስተያየት ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። የትግራይ መምህራን ማሕበር በፌደራሉ መንግስት እና የክልሉ ግዚያዊ አስተዳደር ላይ የመሰረተው ክስ በዚህ ሳምንት በትግራይ ከፍተኛ ፍርድቤት እንደሚታይ ከጠበቆች ሰምተናል።

DW

Addis Admass

05 Nov, 19:58


https://web.facebook.com/100064311447035/videos/546552341445648

Addis Admass

05 Nov, 19:40


100 ሺህ ብር ጉቦ ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል የተባለ የፌደራል ፖሊስ መርማሪ ላይ ክስ ተመሰረተ
የጉዞ እግድ አስነሳለሁ በማለት 100 ሺህ ብር ጉቦ ሲቀበል በቁጥጥር ስር ውሏል የተባለው የፌደራል ፖሊስ መርማሪ ላይ ክስ ተመሰረተ።
የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሽ ዳዊት ሀይለማሪያም ወልደጊዮርጊስ ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ አንቀጽ 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 10 ንዑስ ቁጥር (1) እና (2) መተላለፍ በሚል ጉቦ መቀበል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦበታል።
በክሱ ላይ እንደተመላከተው፤ ተከሳሹ በኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል ምርመራ ቢሮ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ መርማሪ ሆኖ ሲሰራ የማይገባውን ጥቅም ለማግኘት በማሰብ ምርመራ እንዲያጣራ ሀላፊነት ተሰጥቶት ከነበረው ላይት ሀውስ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል/ማህበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ተጠርጣሪ እና በስራቸውም አትሌት የሆኑት 1ኛ የዐቃቤ ሕግ ምስክር ከሀገር እንዳይወጡ የተጣለባቸው የጉዞ እግድ ወደ አሜሪካ ለውድድር ለመሄድ እንዲነሳላቸው በመስከረም 28 ቀን 2017 ዓ.ም ለፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት አቤቱታ ሲያቀርቡ የጉዞ እግዱ እንዲነሳ ለማስደረግ በሚል አስተያየት ለፍርድ ቤቱ እንዲቀርብ 800 ሺህ ብር እንዲከፍሉት ጠይቋል።

Addis Admass

05 Nov, 19:40


በዚህም ተከሳሹ የጉዞ እግድ አስነሳለሁ በማለት በመስከረም 29 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት ገደማ በቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ልዩ ቦታው ገነት ሆቴል ፊት ለፊት ከ1ኛ የዐቃቤ ሕግ ምስክር ተሽከርካሪ ውስጥ 100 ሺህ ብር ተቀብሎ ሲወጣ በፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን የክትትል ባለሙያዎች እጅ ከፍንጅ የተያዘ መሆኑ ተጠቅሶ ጉቦ በመቀበል ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ቀርቦበታል፡፡
ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ከክስ ዝርዝሩ ጋር የሰውና የሰነድ ማስረጃን አያይዞ ያቀረበ ሲሆን ተከሳሹም ዛሬ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ቀርቦ የክስ ዝርዝሩ ከደረሰው በኋላ ከጠበቃ ጋር ተማክሮ ለመቅረብ በይደር ለነገ ተቀጥሯል።
ግለሰቡ በሌላ መዝገብ በተጠረጠረበት የሙስና ወንጀል ጉዳይ የምርመራ ማጣሪያ ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል።
(ኤፍ ቢ ሲ)

Addis Admass

05 Nov, 19:12


በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላንን ትናንት ከኤርባስ ኩባንያ የተረከበ ሲሆን፤ በዛሬው እለትም አውሮፕላኑ አዲስ አበባ ገብቷል፡፡

Addis Admass

05 Nov, 19:01


ክራፍት ሶሉሽን ፋውንዴሽን በነጻ ያሰለጠናቸውን
ከ80 በላይ ወጣቶች ዛሬ አስመረቀ


• ለተማሪዎች ሥልጠና የሚውል ICT BUS እየተጠቀመ ነው


ክራፍት ሶሉሽን ፋውንዴሽን በሶፍትዌር ዴቨሎፕመንት፣በዌብ ዲዛይን፣በግራፊክስ ዲዛይን እንዲሁም ቢዝነስና አንተርፕሩነርሺፕ ያሰለጠናቸውን ከ80 በላይ ወጣቶች በዛሬው ዕለት ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም በደራርቱ ቱሉ የመሰናዶ ት/ቤት አስመረቀ፡፡

ወጣቶቹ ከየካ ክ/ከተማና ከአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ የተውጣጡና ሥልጠናዎቹን ከ3 – 6 ወራት በነጻ የወሰዱ መሆናቸው ታውቋል፡፡

ተቋሙ በዘንድሮው ዓመት በተለየ መልኩ የሶላር ፓወርድ ኮምፒዩተር ባስ (ICT BUS) በመጠቀም ወጣቶቹን በተለያዩ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፎች ማሰልጠኑ ተነግሯል፡፡

ክራፍት ሶሉሽን ፋውንዴሽን፤ መቀመጫውን በኬንያ ናይሮቢ ላይ አድርጎ በትምህርትና ሥልጠና በተለይ ደግሞ በሴቶች፣ ወጣቶች፣ ህጻናትና ልዩ ክህሎት ያላቸው አምራች

የህብረተሰብ ክፍሎችን በኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ ዘርፍ ነጻ ትምህርትና የስልጠና አገልግሎት በተለያዩ አገራት እየሰጠ የሚገኝ፣ ለትርፍ ያልተቋቋመ ዓለማቀፍ ግብረሰናይ ተቋም ነው፡፡

ተቋሙ ይህንን ትምህርትና ስልጠና በኬንያ፣ ኡጋንዳና ህንድ አሁን ላይ ደግሞ በኢትዮጵያ እየሰጠ የሚገኝ ሲሆን፤ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ከሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ለስልጠናው ብቁ የሆኑ ወጣቶችን ከየወረዳውና ክ/ከተማው ተመልምለው በሚቀርቡለት መሰረት በቤዚክ ኮምፒዩተር ስኪል እና አድቫንስድ ኮምፒዩተር ስኪል እንዲሁም ሌሎች አጫጭር ስልጠናዎች ዘርፍ ከ3-6 ወራት በነጻ አሰልጥኖ ያስመርቃል ተብሏል፡፡

Addis Admass

04 Nov, 14:55


በ2ኛ ክስ ደግሞ በሁለቱም ተከሳሾች ላይ እንደቀረበው በግል ተበዳይ ግለሰቧ 200 ዶላር ለ1ኛ ተከሳሽ እንዲከፈለው በማድረግ እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽ የሚያስተዳድረዉ ሆቴል ውስጥ ግለሰቧ ወደ ሃገሯ እንዳትመለስ የጉዞ ሰነዶቿን በመያዝ ናድያ ለተባለች የአባቷ ስም ለማይታወቅ ግብረአበሩ በማስተላለፍ ግለሰቧ በምታስተዳድረዉ ማርኮፖሎ በተባለ ሆቴል ዉስጥ ለሆቴል አገልግሎት ከሚመጡ ደንበኞቹ ጋር የአልኮል መጠጦችን እንድትጠጣ፤ ዝሙት እና መሰል የወሲብ ተግባራትን እንድትፈፅም ማድረጋቸው በክሱ ተጠቅሷል።

በተለይም በባህሬን መቆየት ከምትችልበት የሶስት ወራት ጊዜ ለተጨማሪ አራት ወራት እንዲራዘም እና ቪዛዋ እንዲቃጠል በማድረግ ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ እንድትችል ቪአይፒ በሚል ቅፅል ስም ከሚታወቅ ግብረአበራቸው ጋር ወሲብ እንድትፈፅም ካደረጓት በኋላ ካደረጓት በኋላ በመጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ሃገሯ የተመለሰች በመሆኑ ተመላክቶ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በሰዉ መነገድ ወንጀል ተከሰዋል፡፡

ከሁለቱ ተከሳሾች መካከል አንደኛ ተከሳሽ በቁጥጥር ስር ውላ ክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳት የተደረገ ሲሆን ሁለተኛ ተከሳሽ በሌለበት ጉዳዩ ሲታይ ቆይቷል።

ፍርድ ቤቱ በግራ ቀኝ የቀረበውን የሰውና የሰነድ ማስረጃና ክርክሮችን መርምሮና አመዛዝኖ ተከሳሾችን ላይ የጥፋተኝነት ፍርድ ሰጥቶ፤ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ 1ኛ ተከሳሽን በ13 ዓመት ጽኑ እስራት 2ኛ ተከሳሽን ደግሞ በ16 ዓመት ጽኑ እስራትና በየደረጃው በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።
ኤፍ ቢ ሲ

Addis Admass

04 Nov, 14:53


የኪነት ባለሙያዋን በውጭ ሀገር ለወሲብ ብዝበዛ ያጋለጡ ተከሳሾች በ13 እና በ16 ዓመት እስራት ተቀጡ

የሙዚቃ ተወዛዋዥ የሆነችውን ግለሰብን በህገወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር በመላክ ለወሲብ ብዝበዛ አጋልጠዋል የተባሉት ተከሳሾች በ13 እና በ16 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጡ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 13ኛ ወንጀል ችሎት ወሰነ።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾቹ ፍሬህይወት ስለሺ እና አሊ ፈርዳን ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣዉን የወንጀል ህግ አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 1 እና አንቀጽ 137 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመላከተውን፣ በሰው የመነገድ እና ሰውን በህገ ወጥ መንገድ ድንበር የማሻገር ወንጀል ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የወጣዉን አዋጅ ቁጥር 1178/2012 አንቀፅ 3 4/ እና አንቀፅ 3/2 ስር የተመለከተዉን ድንጋጌ መተላለፍ የሚል ተደራራቢ ክሶችን አቅርቦባቸዋል።

በዚህ በቀረበባቸው በአንደኛ ክስ ላይ እንደተመላከተው 1ኛ ተከሳሽ ካልተያዙ ግብረአበሮች ጋር በመሆን ከኢትዮጵያ የግዛት ክልል ዉጪ ወደ ባህሬን ለስራ መላክ በሚል ሽፋን የዘመናዊ እና ባህላዊ ዘፈን ተወዛዋዥ የሆነችዉን የግል ተበዳይ “ዘመናዊ እና ባህላዊ ዉዝዋዜ እየሰራሽ በየወሩ 500 ዶላር ይከፈልሻል፣ ምግብ እና መኝታ በጥሩ ሁኔታ ታገኛለሽ ትርዒት ስታቀርቢ ትሸለሚያለሽ” በማለት በማታለል ወደ ባህሬን በመውሰድ ቪአይፒ በሚል ቅፅል ስም ከሚታወቅ ግብረአበር ጋር ወሲብ እንድትፈፅም ማድረጋቸው በክስ ዝርዝሩ ላይ ተጠቅሶ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በሰው መነገድ ወንጀል ተከሰዋል።

⬇️⬇️

Addis Admass

02 Nov, 12:52


ሩሲያ ጉግል ላይ የጣለችው የገንዘብ ቅጣት፣
ዓለም ቢተባበርም አይከፍለውም

• 20,000,000,000,000,000,000,000,000,000,000,000 ዶላር ነው


ሩሲያ በቢሊየነሩ የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኩባንያ - ጉግል ላይ ከሰሞኑ የጣለችው የገንዘብ ቅጣት እንኳንስ ኩባንያው መላው ዓለም ቢተባበርም ሊከፍለው አይችልም ነው የተባለው፡፡

የሩሲያው ፍርድ ቤት የአገሪቱ ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ዩቲዩብ ላይ እንዳይታዩ በመታገዳቸው ጉግል፣ ሁለት አንዲሲሊዩን ሩብል እንዲከፍል ወስኖበታል።

አንዲሲሊዮን 36 ዜሮዎች ያሉት ቁጥር ነው። ጉግል በሩሲያው ፍርድ ቤት እንዲከፈል የተፈረደበት የገንዘብ ቅጣት በዶላር ሲመነዘር፤20,000,000,000,000,000,000,000,000,000,000,000 ዶላር ነው ተብሏል፡፡

ሁለት ትሪሊዮን የሚገመት ሃብት እንዳለው የሚነገርለት ጉግል፤ ምንም እንኳ ከዓለማችን እጅግ ሀብታም ኩባንያዎች አንዱ ቢሆንም፣ ይህን የሚያህል ገንዘብ የመክፈል አቅም እንደሌለው ተዘግቧል፡፡

ጉጉል ክፈል የተባለው ገንዘብ ከዓለማችን አገራት ጠቅላላ ያልተጣራ ምርት (ጂዲፒ) በላይ መሆኑን ያመለከተው ቢቢሲ፤ የዓለማችን ጠቅላላ ያልተጣራ ምርት 110 ትሪሊዮን ዶላር መሆኑን ዓለማቀፉን የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ጠቅሶ ዘግቧል፡፡

የሩሲያ መንግሥት የዜና ወኪል - ታስ እንደዘገበው፤ ገንዘቡ እንዲህ የተጋነነ ሊሆን የቻለው ቅጣቱ በየጊዜው እየጨመረ በመምጣቱ ነው።

የክሬምሊን ቤተመንግሥት ኑ ቃል አቀባይ ዲምትሪ ፔስኮቭ፤ “ይህ ቁጥር እንዴት እንደሚጠራ እንኳን አላውቀም” ማለታቸውን የጠቆመው የዜና ወኪሉ፤“ሆኖም የጉግል ኃላፊዎች ለጉዳዩ ትኩረት እንዲሰጡት” ማሳሰባቸውን ዘግቧል፡፡

አርቢሲ የተባለው የሩሲያ በይነ መረብ በበኩሉ፤ ጉግል ቅጣቱ የተላለፈበት 17 የሩሲያ የዜና ጣቢያዎች ዩቲዩብ ላይ ይዘታቸውን እንዳያስተላልፉ እገዳ ስለተጣለባቸው ነው ብሏል፡፡

የይዘት ቁጥጥሩ የተጀመረው እ.ኤ.አ በ2020 ቢሆንም፣ ከሁለት ዓመታት በኋላ ሩሲያ ዩክሬን ላይ ወረራ ስትጀምር ሁኔታዎች እየተካረሩ መምጣታቸው ይነገራል፡፡

የሩሲያ መገናኛ ብዙኃን በአውሮፓ ሀገራት መታገዳቸውን ተከትሎ፣ ሞስኮም የአጸፋ እርምጃ መውሰድ ጀምራለች። እ.ኤ.አ በ2022 በሩሲያ የጉግል ወኪል ኩባንያ መክሰሩን ሲያስታውቅ፣ ጉግል ደግሞ በሩሲያ ማስታወቂያን ጨምሮ ሌሎች የንግድ ሥራዎችን ማከናወን ማቆሙን አስታውቋል። ነገር ግን የጉግል ምርቶች ሙሉ በሙሉ ሩሲያ ውስጥ አገልግሎት መስጠት አላቆሙም ነበር።

አሁን በአሜሪካው ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያና በሩሲያ መካከል ያለው ውጥረት በገንዘብ ቅጣቱ ምክንያት እንደ አዲስ ማገርሸቱ ተነግሯል፡፡ እ.ኤ.አ በግንቦት 2021 የሩሲያ የመገናኛ ብዙኃን ተቆጣጣሪ ድርጅት፣ ጉግል የሩሲያ ሚዲያዎች በዩቲዩብ እንዳይተላለፉ እያደረገ ነው ሲል መውቀሱ አይዘነጋም።

በዩቲዩብ ላይ ይዘታቸው ከታገደባቸው ጣቢያዎች መካከል ደግሞ በመንግሥት ቁጥጥር የሆኑት አርቲ እና ስፑትኒክ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በሐምሌ 2022 ሩሲያ ጉግል ላይ የ21.1 ቢሊዮን ሩብል (301 ሚሊዮን ዶላር) የገንዘብ ቅጣት መጣሏ ይታወሳል፡፡ ቅጣቱ የተወሰነውም ጉግል በዩክሬን ጦርነት ምክንያት የተወሰኑ ይዘቶች እንዳይተላለፉ በማድረጉ ነበር፡፡

የሆኖ ሆኖ አሁን ሩሲያ በጉጉል ኩባንያ ላይ የጣለችው የገንዘብ ቅጣት በኩባንያው አቅም የሚከፈል አይደለም - ያን ያህል ገንዘብ እንኳንስ ኩባንያው የዓለም አገራትም እንደሌላቸው ነው የተነገረው፡፡

የገንዘቡ መጠን ለቁጥር መማሪያ ይጠቅም እንደሆነ እንጂ ዓለም ይሄን ያህል ገንዘብ የላትም ተብሏል፡፡ እስቲ የቁጥሩን ርዝመት ደግመን እንመልከተው - 20,000,000,000,000,000,000,000,000,000,000,000 ዶላር፡፡

አንድ ነገር ግን መጠርጠር ይቻላል፡፡ በዓለም ታሪክ በአንድ ኩባንያ ላይ የተላለፈ እጅግ ከፍተኛው የገንዘብ ቅጣት ተብሎ በዓለም የድንቃድንቆች መዝገብ ላይ የመስፈር ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡

Addis Admass

01 Nov, 20:03


ውድ አንባቢያን

ሳምንታዊ የቅዳሜ ጋዜጣችሁን አዲስ አድማስን፣ በእነዚህ
የመዲናችን መፃሕፍት መደብሮች ውስጥ እንደምታገኙት
ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
• ጃፋር መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ)
• ክብሩ መፃሕፍት መደብር (ጥቁር አንበሳ፣ ትራኮን ህንጻ)
• እነሆ መፃሕፍት መደብር (አራት ኪሎ)
• ኢዞጵ መፃሕፍት መደብር (አቡነ ጴጥሮስ)
• አምደ መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ) አዲስ አድማስ የእርስዎና ቤተሰብዎ

Addis Admass

01 Nov, 19:59


🟠 በማለዳ ይጠብቁን!! 🟠

Addis Admass

01 Nov, 19:36


ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም

በዛሬዋ_ዕለት

ከ 94 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የንግሥ በዓል ዋዜማ ፤ የንጉሠ ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለበዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ (ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ የተመረቀበት ዕለት ነበር።

ታሪክን_ወደኋላ

Addis Admass

01 Nov, 18:08


የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ከ200 በላይ
ዘመናዊ (Smart) ቅርንጫፎችን ከፈተ


የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ ፊቱን ወደ ዲጂታል ባንኪንግ ማዞሩን የገለጸ ሲሆን፤ በዚህ ረገድም ከ200 በላይ ዘመናዊ (Smart) ቅርንጫፎችን በመላ አገሪቱ መክፈቱን አስታውቋል፡፡

ባንኩ ያስተዋወቀው አዲሱ አገልግሎት ደንበኞች ለዚሁ ዓላማ የተዘጋጁ ታብሌቶችን በመጠቀም ከወረቀት ነጻ በሆነ መንገድ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል።

ባንኩ ትናንት እንዳስታወቀው፤ ስማርት ቅርንጫፎቹ በዲጂታል መንገድ ገንዘብ ማስገባት፣ ማውጣትና ማዛወርን የመሳሰሉ አገልግሎቶችን ከልማዳዊው ወረቀት ተኮር አሰራር በተለየ መንገድ ማግኘት ያስችላሉ፡፡

ከተመሰረተ ከ19 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንክ፤ በአሁኑ ወቅት ወደ 13 ሚሊዮን የሚጠጉ የሂሳብ ባለቤቶች ያሉት ሲሆን፤ በአገር አቀፍ ደረጃ ከ750 በላይ ቅርንጫፎችን ከፍቷል፡፡

Addis Admass

01 Nov, 17:55


የፓን አፍሪካን የሴቶች አመራርና ለውጥ ላይ
የሚመክር ግዙፍ ጉባኤ በመዲናዋ ተካሄደ


የፓን አፍሪካን የሴቶች አመራርና ለውጥ ላይ የሚመክር ግዙፍ ጉባኤ፣ በዛሬው ዕለት ከጠዋት ጀምሮ በአዲስ አበባ ራዲሰን ሆቴል ተካሂዷል፡፡

በጉባኤው ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ሓላፊዎች መሳተፋቸው ታውቋል፡፡

የዘንድሮ የ2024 የፓን አፍሪካ አመራር ጉባኤ፣ አፍሪካ በምታደርገው ጉዞ፣ የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎና አመራር በአህጉሪቱ እንዴት ማስተዋወቅ እንደሚቻል በጋራ መክረዋል ተብሏል፡፡

በዚህ ጉባኤ የምንፈልጋት አፍሪካ፣ በሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎ እንዴት ማንጸባረቅ፣ማሰብ እንደገና መገመትና ማቀድ ይቻላል በሚለው ጉዳይም ላይ ውይይት መደረጉ ተመልክቷል፡፡

ጉባኤው በተጨማሪም ሴቶች እንዴት ፍትሃዊና አካታች አመራርን መገንባትና ማበርታት አለባቸው የሚለውንም መንገድ ያሳያል ነው የተባለው፡፡

ከጉባኤው አዘጋጆች በተገኘው መረጃ መሰረት፣ በዚህ ታላቅ የጉባኤ መድረክ ላይ የፖለቲካ መሪዎች፣ የፓን አፍሪካን ምሁራን፣ የሴቶች መብት ተሟጋቾች፣ መሪ የሴት ባለሙያዎች፣ በጎ አድራጊዎች፣ ፖሊሲ አውጭዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ዓለማቀፍ መሪዎች፣ አክቲቪስቶች፣ አካል ጉዳተኞችና ሌሎች ከፍተኛ ሃላፊዎች ተሳትፈውበታል፡፡

ለአንድ ቀን በራዲሰን ብሉ ሆቴል የተካሄደውን ይህን ጉባኤ፤ አኪና ማማ ዋ አፍሪካ ፣ ከሥርዓተ-ጾታ ”የእኔ ዘመቻ“ በሚል ኔትዎርክ፣ የአፍሪካ ሴቶች ልማትና ኮሙዩኒኬሽን እንዲሁም የታንዛኒያ ጾታ ጉዳይ ትስስር በጋራ እንዳዘጋጁት ለማወቅ ተችሏል፡፡

Addis Admass

01 Nov, 17:45


የወጫሌ ወረዳ አስተዳዳሪን ጨምሮ ከ50 በላይ
የመንግሥት የጸጥታ ሃይሎች መገደላቸው ተሰማ


በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን፣ የወጫሌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጉሤ ኮሩን ጨምሮ ከሃምሳ በላይ የሚሆኑ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ዛሬ ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም ማለዳ ላይ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራው አማጺ ቡድን በተከፈተባቸው ጥቃት መገደላቸውን ዋዜማ ሬዲዮ ምንጮቿን ጠቅሳ ዘግባለች፡፡

የወረዳው አስተዳዳሪ፣ የዞን አመራሮች እንዲሁም በርካታ የመንግሥት ታጣቂዎች አማጺ ቡድኑ በስፋት ይንቀሳቀሳል ወደሚባልበት ካራ ተብሎ ወደሚጠራው ስፍራ ዛሬ ማለዳ 12 ላይ ለጸጥታ ስራ ተሰማርተው እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

በስፍራው እንደደረሱም ታጣቂ ቡድኑ በከፈተባቸው ድንገተኛ ጥቃት የወረዳ አስተዳዳሪውን ጨምሮ ከሃምሳ በላይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች ወዲያው ሕይወታቸው ሲያልፍ፣ የወረዳው የሚሊሻ ጽ/ቤት ኃላፊውን ጨምሮ በርካቶች ደግሞ ቆስለው ወደ ሙከጡሪ ሆስፒታል መወሰዳቸውን ዋዜማ አረጋግጣለች፡፡

በጥቃቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ከሙከጡሪ ሆስፒታል ሪፈር ተጽፎላቸው ወደ አዲስ አበባ መምጣታቸውን የገለጹት የአካባቢው ምንጮች፣ የሟቾች ቁጥር ከዚህም ሊያሻቅብ እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡

አቶ ንጉሤ ኮሩ ከዚህ ቀደም በዞኑ የአለልቱ ወረዳ አስተዳዳሪ በመሆን፣ በዞኑ ደግሞ በተለያዩ ኃላፊነት ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፣ በቅርቡ ደግሞ የወጫሌ ወረዳ አሥተዳዳሪ ሆነው መሾማቸውን ለመረዳት ተተችሏል፡፡

Addis Admass

01 Nov, 11:28


የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው ከ1700 ሊትር የምግብ ዘይትና ሌሎች የምግብ ሸቀጣሸቀጦች ለገበያ ሊቀርቡ ሲሉ በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ዋለ።
የአገልግሎት ግዜ አልፎባቸው እንዲወገዱ የተደረጉ ዘይት ወተት፣ ድቄት እና ሩዝ ከተቀበሩበት በማውጣት ለሽያጭ ሊውሉ ሲል ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት መያዙን የአዲስ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ዋ/ኢ/ር ብስራት ጫኔ አስታውቀዋል ።
ዋኢ/ር ብስራት ጫኔ እንደገለፁት በከተማችን ድሬዳዋ ቀፊራ እየተባለ በሚጠራው የገበያ ስፍራ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችል የአገልግሎት ግዜ ያለፈባቸው ለምግብነት እንዳይውሉና የተወገዱ ዘይት፣ ወተት ዱቄት እና ሩዝ ተወግዶ የነበረበትን ጉድጓድ ቆፍሮ በማውጣት ለመሸጥ በመዘጋጀት ላይ እንዳሉ በህብረተሰቡ ጥቆማ መሰረት በአዲስ ከተማ ፖሊስ ጣቢያና በመጋላ ፖሊስ ጣቢያ በተሰራ ቅንጅታዊ ስራ 10 ሴት እና 7 ወንድ ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት ያላቸውን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል ።
ዋ/ኢ ብስራት ጫኔ ህብረተሰብ ከፖሊስ ጋር ያደረገውን ትብብር አመስግነው ለምግብነት የሚውሉ ግብአቶችን ሲገዛ የአገልግሎት ግዜ አለማለፉን በማረጋገጥ ጤናውን መጠበቅ እንዳለበት አስታውቀው መሰል ድርጊት ፈፃሚዎችን በሚመለከት ለፖሊስ ጥቆማ የመስጠት ተግባሩን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ።

ድሬ ፖሊስ

Addis Admass

01 Nov, 11:21


የኮሪደር ልማቱ የኢትዮጵያን ስም ከፍ ያደርጋል- ጋዜጠኞች
የመዲናዋ የኮሪደር ልማትና ውብ የቱሪዝም መዳረሻዎች የኢትዮጵያን ስም ከፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን የተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ጋዜጠኞች ገለጹ።
"ሚዲያ ለብሔራዊ ትርክትና ሀገር ግንባታ" በሚል መሪ ሐሳብ ለመገናኛ ብዙኃን አመራሮችና ባለሙያዎች ለሦስት ቀናት ስልጠና ተሰጥቷል፡፡
በስልጠናው ማጠናቀቂያም የብሔራዊ እዮቤልዩ ቤተ-መንግሥት እድሳትን ጨምሮ በአዲስ አበባ የተከናወኑ እና በመከናወን ላይ ያሉ የኮሪደር ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።
በዚሁ ወቅት ለኢዜአ አስተያየታቸውን የሰጡ ጋዜጠኞች እንደገለጹት÷ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ትናንትን፣ ዛሬን እና ነገን በማስተሳሰር የሚያሳዩ ናቸው፡፡
በመንግሥት ቃል የተገቡ ሥራዎች በተጨባጭ መሬት ላይ መውረዳቸውን ተመልክተናል ሲሉም ገልጸዋል፡፡
የቱሪዝም ዘርፍ ለሀገር ዕድገት የድርሻውን እንዲወጣ በመንግሥት የተገነቡ ውብ የመስኅብ ስፍራዎችን መገናኛ ብዙኃን ማስተዋወቅ እንደሚጠበቅባቸውም አመላክተዋል፡፡
አዲስ አበባን ለዓለም እና አኅጉራዊ ጉባዔዎች ተመራጭ የሚያደርጉ የቱሪዝም መዳረሻዎች መገንባታቸውንም ተመልክተናል ነው ያሉት፡፡

Addis Admass

01 Nov, 08:53


ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከ2 ሺህ በላይ መጻሕፍትን ለአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት አበረከቱ

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በዛሬው እለት ቁጥራቸው ከ2 ሺህ በላይ የሆኑ መጻሕፍትን እና 25 “ኦርካም ማይ አይ” የተባለ ዐይነ ስውራን አንባቢያንን የሚያግዝ መሳሪያ ለአብርሆት ቤተ-መጻሕፍቱ በስጦታ አበርክተዋል፡፡
ለቤተ መጻሕፍቱ የተበረከቱት መጻሕፍት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ለአንባቢያን በተለይ ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጠቅላላ እውቀትን የሚሰጡ የመጻሕፍት ስብስብ መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡
መጻሕፍቱ “Book for Africa” ከተባለ ድርጅት በድጋፍ የተገኙ መሆናቸው መገለፁን ከቀዳማዊት እመቤት ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Addis Admass

01 Nov, 08:28


የጋሽ ማህሙድ አሕመድ የግማሽ ክ/ዘመን
የሙዚቃ ጉዞ፣ በታላቅ ኮንሰርት ሊቋጭ ነው
*የህይወት ታሪክ መጽሐፉ ይመረቃል፤ ሃውልት ይቆምለታል

*በስሙ መንገድ ይሰየማል፤የመጨረሻው ሲዲ ይለቀቃል

የጋሽ ማህሙድ አሕመድ የመጨረሻ የሙዚቃ መድረክ በሚሊኒየም አዳራሽ ሊካሄድ መሆኑ ተገልጿል። በዚህ የሙዚቃ መድረክ ላይ ጥቂትና የተመረጡ ድምጻውያን ስራዎቻቸውን እንደሚያቀርቡ ተነግሯል።

ትናንት ጥቅምት 22 ቀን 2017 ዓ.ም. በሸራተን አዲስ ሆቴል፣ ላሊበላ አዳራሽ ስለ ኮንሰርቱና ስለ አንጋፋው ድምጻዊ የሙዚቃ ህይወት ስንብት ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ የሙዚቃ ባለሙያው አርቲስት አብርሃም ወልዴ፣ የጆርካ ኤቨንት ኦርጋናይዘር መስራችና ባለቤት አቶ አጋ አባተን ጨምሮ ሌሎች አባላትን ያካተተው የመርሃ ግብሩ አስተባባሪ ኮሚቴ በመግለጫው ላይ እንዳብራራው፤ “ሰው በሕይወት እያለ የማመስገንና የማክበር ባህልን ለመጀመር ጋሽ ማህሙድ ትክክለኛ ሰው ነው።” ብሏል፡፡ ኮሚቴው አክሎም፤ “ታላቅን ማክበር በተዘነጋበት ዘመን ዝቅ ብሎ ታናሹን የሚያከብር ሰው” መሆኑ ለተመሰከረለት ጋሽ ማህሙድ፤ በህይወት እያለ ማክበርና ማመስገን ተገቢ እንደሆነ የኮሚቴው አባላት አስረድተዋል፡፡

በዚሁ መግለጫ እንደተነገረው፤ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. “ደረጃውን የጠበቀ የሙዚቃ ኮንሰርት” በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ የሚካሄድ ሲሆን፤ 25 ሺ ሰዎች ይታደሙበታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ከኮሚቴው አባላት አንዱ የሆነው አርቲስት አብርሃም ወልዴ ኮንሰርቱን በተመለከተ በሰጠው ማብራሪያ፤ “የጋሽ ማህሙድን ክብር በጠበቀ ሁኔታ፣ ጥቂት ነገር ግን ምርጥ ድምጻውያን የሚያቀነቅኑበት መድረክ ነው የሚሆነው” ሲል ተናግሯል።

Addis Admass

01 Nov, 08:23


የአንጋፋው ድምጻዊ ማህሙድ አህመድ የመድረክ ስንብት የመጨረሻ ኮንሰርት ጋዜጣዊ መግለጫ በሸራተን አዲስ እየተሰጠ ነው

Addis Admass

31 Oct, 19:53


"ባደረግነው የቤተመንግስት ዕድሳት ተቆልፎበት የተቀመጠ 400 ኪሎ ግራም ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ አስገብተናል"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Addis Admass

30 Oct, 18:43


https://youtu.be/g1Vo26dQNzo

Addis Admass

30 Oct, 18:37


ቱሪዝም ለሀገራዊ አንድነት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ።

የቱሪዝም ሚንስቴር ሚኒስትር ክብርት ሰላማዊት ካሳ ከኢትዮጵያ የቱሪስት አስጎብኚ ፣ ከኢትዮጵያ ባህል እና ቱሪዝም ጋዜጠኞች ማህበራት እና ከኃይኪንግ ኦርጋናይዘር አሶሴሽን ተወካዮች ጋር ተወያይተወል።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የማህበራቱ ተወካዮች ለቱሪዝም ለዘርፉ እድገት ሙያቸው በሚፈቅደው አግባብ አስተዋፆ እያደረጉ እንደሆነ ገልፀዋል። ይሁንና በሥራ ሂደት የሚያጋጥሙ ተግዳሮቶችን ከተቋሙ ጋር ተቀራርቦ በመስራት ለተገቢው ውጤትም እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል፡፡

ክብርት ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በበኩላቸው ማህበራቱ የሀገር ውስጥ ቱሪዝም እንዲስፋፋ ከሚጫወቱት ሚና ባሻገር እርስ በርስ መተዋወቅን በማስፋት ለሀገራዊ አንድነት ቱሪዝም ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያመጣ በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻ ክብረት ሚኒስትሯ ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚደረጉ መሰል መድረኮች የእርስበርስ ትብብር መንፈስንም የበለጠ እንደሚጨምር ገልጸዋል፡፡

Addis Admass

30 Oct, 15:07


በመገናኛ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የትራንስፖርት መጨናነቅ ለመፍታት ያግዛል የተባለ የመሬት ውስጥ የእግረኛ መተላላፊያ መስመር ግንባታ ተጀመረ፡፡

Addis Admass

30 Oct, 14:58


ኢትዮጵያዊው ባለሃብት ሼክ አሊ ሁሴን ታሰሩ


የአልፎዝ ኃ.የተ.የግ.ኩባንያ ባለቤት የሆኑት ሼክ አሊ ሁሴን በትላንትናው ዕለት ማክሰኞ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም መታሰራቸው ተነገረ፡፡

አልፎዝ፤ ቡናን ጨምሮ ሌሎች ምርቶችን ወደ ውጭ በመላክ የሚታወቅ ኩባንያ ሲሆን፤ አሊ ሁሴን የአቢሲኒያ ባንክን ጨምሮ የብዙ ባንኮች ዋነኛ ባለድርሻ ናቸው፡፡

ኢንቨስተሩ በትላንትናው ዕለት በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን፤ የታሰሩበት ምክንያት እስካሁን አልተገለጸም፡፡

Addis Admass

30 Oct, 09:47


በወላይታ ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ7 ሰዎች ሕይወት አለፈ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ካዎ ኮይሻ ወረዳ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሸራተት አደጋ የ7 ሰዎች ሕይዎት አለፈ።
በወረዳው ላሾ እና 01 ቀበሌዎች የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው የመሬት መንሸራተት አደጋ ከሟቾች በተጨማሪ በሁለት ሰዎች እና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿል።
በዞኑ የካዎ ኮይሻ ወረዳ ዋና አስተዳደሪ አቶ አበባየሁ ዮሐንስ የስጋት ቀጠናዎች ላይ አሁንም ሕብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ማስገንዘባቸውን የወላይታ ዞን ኮሙኒኬሽን ዘግቦታል፡፡

Addis Admass

29 Oct, 11:38


ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ እያመረተ ለገበያ በማቅረብ ላይ የሚገኘው “ታይ ታይ” ከረሜላዎች እና “ሎሊ ፖፕ” ምርቶቹ ሕጋዊ ምርቶች መሆናቸውን አስታውቋል። የድርጅቱ ኦፕሬሽናልና ማርኬቲንግ ማኔጀር አቶ ኢዮኤል ጥበቡ እንደተናገሩት፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በኢትዮጵያ ገበያ ተመሳሳይ ምርቶች መታየታቸውን ጠቁመዋል።

አቶ ኢዮኤል እነዚሁ ምርቶች የሚመረቱበት ቦታ ካለመታወቁ ባሻገር የሚጠቀሙት ግብዓት ምንነት ያልተረጋገጠ መሆኑን አንስተው፣ ከጤና አንጻር የአደጋ ስጋት “ናቸው” ብለዋል። ከዚህም ባሻገር በሕጋዊ ኢንቨስተሮች ላይ ከፍተኛ አሉታዊ ተጽዕኖ “ይፈጥራሉ” ሲሉ አስረድተዋል።

“ሕገ ወጦቹ አስር ብር ቀንሰው ተመራጭ ለመሆን እየታገሉ ነው።” በማለት ጉዳዩን የሚያብራሩት የድርጅቱ ኦፕሬሽናልና ማርኬቲንግ ማኔጀር፣ “ኪሳራው ‘ይህን ያህል ነው’ ባንልም፣ [ሕገ ወጦቹ] ገበያ እየተሻሙ ነው።” ብለዋል።

ጉዳዩን ለመንግስት እና ለሚመለከታቸው አካላት “አሳወቀናል” ያሉት አቶ ኢዮኤል፣ ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ለምርቶቹ ተጠቃሚዎች፣ የንግድ መደብር ባለቤቶች እና ወላጆች ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ምርት የሆነው “ታይ ታይ” ከረሜላ ብቻ ዋናውና የተመሰከረለት ምርቱ መሆኑን ማረጋገጥ እንደሚያሻ ነው ያስታወቁት። የንግዱ ማሕበረሰብ ተረክቦ ስለሚሸጠው ምርት ሃላፊነት መውሰድ እንዳለበት አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

መቀመጫውን ቱርክ ያደረገውና በኢትዮጵያ በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2018 ምርት የጀመረው ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ፣ “ታይ ታይ” የተሰኘው ከረሜላ የዓለምአቀፍ ደረጃን በመጠበቅ የሚያመርት ሲሆን፣ ሌላኛው “ሎሊፖፕ” የተሰኘው ታዋቂ ምርቱም “በማንኛውም ዕድሜ ላይ ለሚገኙ ሁሉ እንዲስማማ ተደርጎ አስተማማኝ ደስታን በሚሰጥ ጣዕም የተዘጋጀ ምርቴ ነው” ሲል ድርጅቱ ጠቅሷል።

Addis Admass

29 Oct, 11:38


ሕገ ወጥ አምራቾች የገበያ ሽሚያ እንደፈጠሩበት ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ገለጸ

ሕገ ወጥ አምራቾች ተመሳሳይ ምርቶችን በማቅረብ የገበያ ሽሚያ እየፈጠሩበት እንደሚገኙ ቪታ ፉድ ኢንዱስትሪ ገልጿል። ድርጅቱ እነዚሁ አምራቾች የሚጠቀሙት ግብዓት ምንነት አለመታወቁ ከጤና አንጻር የአደጋ ስጋት መሆናቸውን አመልክቷል።

Addis Admass

29 Oct, 08:55


የ”ዳሽን ከፍታ” የስራ ፈጠራ ቅድመ ውድድር ስልጠና ተሰጠ

በዳሽን ባንክ የተዘጋጀው፣ ሶስተኛው ምዕራፍ የ”ዳሽን ከፍታ” የስራ ፈጠራ ቅድመ ውድድር ስልጠና በአዲስ አበባ ከተማ፣ ኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ተሰጥቷል። በዚሁ ስልጠና ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የመጡ ወጣቶች ተሳታፊ ሆነውበታል።

ዛሬ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ የተሰጠው ይኸው ስልጠና፣ የስራ ፈጠራ ሃሳብ ያላቸው ተወዳዳሪዎች ሃሳባቸውን በምን መልኩ ማቅረብና ወደ ስራ መቀየር እንዳለባቸው የሚያግዝ ስለመሆኑ ተገልጿል። እንዲሁም በስራ ፈጠራ ጽንሰ ሃሳብ፣ በፈጠራ ንድፈ ሃሳብ አዘገጃጀት እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይም ስልጠናው ትኩረቱን አድርጎ እንደተሰጠ ተጠቁሟል።

በዘንድሮው የቅድመ ውድድር ስልጠና ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በባሕር ዳር፣ ደሴ፣ መቐለ፣ አዳማ፣ ድሬዳዋ፣ ወላይታ፣ ሃዋሳና ጅማ ከተሞች የተሰጠ ሲሆን፣ ስልጠናው ከተሰጠ በኋላ ሰልጣኞቹ የፈጠራ መነሻ ሃሳባቸውን በፅሑፍ በባንኩ ቅርንጫፎች በኩል እንዲያቀርቡ “ይደረጋል” ተብሏል።

አስተያየታቸውን የሰጡ ሰልጣኞች፣ ከስልጠናው በርካታ ከስራ ፈጠራ ጋር የተያያዙ የመፍትሄ ሃሳቦችን “አግኝተንበታል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ዳሸን ባንክ እስከ አሁን ባካሄደው በ”ዳሽን ከፍታ” የስራ ፈጠራ ውድድር በመጀመሪያውና ሁለተኛው ዙር በሺሕዎች የሚቆጠሩ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ወጣቶች በስልጠና እና ውድድር መርሐ ግብሮች ሲሳተፉ፣ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑት የ”ዳሽን ከፍታ” የስራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊዎች በባንኩ የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎላቸው ስኬታማ ስራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኙ ከባንኩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

Addis Admass

29 Oct, 07:59


ኢትዮ ቴሌኮም አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን የሳይበር ጥቃት ሙከራ ማክሸፉን ገለጸ

ኢትዮ ቴሌኮም አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን የሳይበር ጥቃት ሙከራ ማክሸፉን ገለጿል። ላለፉት 130 ዓመታት በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ኢትዮ ቴሌኮም የሳይበር ደህንነት ለማረጋገጥ ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ጋር ምክክር እያካሄደ በትናንትናው ዕለት ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ.ም. አካሂዷል።

በዓለም ለ21ኛ፣ በኢትዮጵያ ለ5ተኛ ጊዜ የሚከበረው የሳይበር ደሕንነት ወር ምክንያት በማድረግ ነው ኢትዮ ቴሌኮም በመረጃ መንታፊዎች በተደጋጋሚ የሳይበር ጥቃት የሚደርስባቸው የፋይናንስ ተቋማት ጥቃቱን ለመከላከል የሚያስችላቸው የምክክር መድረክ እያካሄደ የሚገኘው።

“የሳይበር ጥቃትን መከላከል የሚችል የዲጂታል ስነ-ምህዳርን መገንባት” በሚል መሪ ሃሳብ ኩባንያው በጋራ ከሚሰራቸው ከፋይናንስ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ጋር የመከረ ሲሆን፣ በምክክሩ የኢትዮጵያ መረብ ደሕንነት አስተዳደር ምክትል ዳይሬክተር ዳንኤታ ጉታ፣ የኢትዮ ቴሌኮም ቺፍ ኦፊሰር አሰግድ አየለ እንዲሁም ከተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት የተወጣጡ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

ከ80 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች በሚጠቀሟቸው የኩባንያው አገልግሎቶች 1 ነጥብ 5 ያህል የሳይበር ጥቃት ሙከራ የተደረገባቸው ሲሆን፣ ጥቃቶቹንም መከላከል እንደተቻለ ተገልጿል።

“ዲጂታል ኢትዮጵያ”ን በ2025 ለማሳካት ውጥን ይዞ የሚንቀሳቀሰው ኢትዮ ቴሌኮም፣ የሚሰጣቸው የፋይናንስ አገልግሎቶች ከሳይበር ጥቃት የፀዳ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ በመድረኩ ተመላክቷል።

የሳይበር ደሕንነትን ለማረጋገጥ ተቋማት “በንቃት ሊሰሩበት የሚገባ ጉዳይ ነው” ያሉት የኢትዮጵያ መረብ ደሕንነት አስተዳደር ምክትል ዳይሬክተር ዳንኤል ጉታ “ስለሚገጥሙ ጥቃቶች በግልጽ በመነጋገር ከሳይበር ጥቃት የፀዳ የፋይናንስ አገልግሎት ለመስጠት ሃላፊነት እና መረጃን መጋራት የግድ ነው” ብለዋል።

የሳይበር ደሕንነት ለማረጋገጥ የሁሉም ፋይናንስ ተቋማት ርብርብ እንደሚያስፈልግ በምክክር መድረኩ በአፅንዖት ተጠቅሷል።

Addis Admass

28 Oct, 12:13


ኖህ ሪልስቴት ዛሬ ያስረከባቸው መኖሪያ ቤቶች መዋኛ ገንዳ፣ የከርሰ ምድር ውሃ እንዲሁም የስፖርት ማዘወተሪያ ያካተቱ መሆናቸውም ተጠቅሷል። የኖህ ሪል ስቴት ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ፍቃዱ አዋሽ ኖህ ሪል ስቴት የመኖሪያ አፓርታማዎችን በጊዜ እና በጥራት በመገንባትና በማጠናቀቅ የደንበኞቹን አመኔታ ያተረፈ ድርጅት ነው ብለዋል። "ያልገነባነውን አንሸጥም" በሚል መሪ ቃሉ የሚታወቀውድርጅቱ በቅርቡ እንቁላል ፋብሪካ አከባቢ "ኖህ አስኳል" በተሰኘ ሳይት ከ750 በላይ መኖሪያ ቤቶችን በአዋሬ ሴቶች አደባባይ አከባቢ "ኖህ ቪክትሪ" በተሰኘ ሳይት 152 ቤቶችን ለቤት ባለቤቶች እንደሚያስረክብ ገልፀዋል።

የድርጅቱ መስራችና ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴዎድሮስ ዘሪሁን በበኩላቸው "የአዲስ አበባን ውበት በሚመጥን መልኩ እስከ 2020 ዓ.ም ድረስ አብዛኛውን የከተማችን ነዋሪዎች ተደራሽ የሚያደርጉና ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው ቤቶች ገንብቶ ለማስረከብ እየሰራን እንገኛለን" ያሉ ሲሆን በቀጣይ ወር ቦሌ ሆምስ አካባቢ ከ5,000 በላይ የሚሆኑ ቤቶችን ግንባታ እንደሚያስጀምሩ ተናግረዋል።

በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ ም/ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ የመኖሪያ ቤቶቹን ከጎበኙ በሗላ ባደረጉት ንግግር በከተማችን ከፍተኛ የሆነ የቤት ፍላጎት አለ ይህ በመንግስት ብቻ ሊሸፈን አይችልም የግል ቤት አልሚዎችን በመደገፍ የነዋሪውን የቤት ፍላጎት መሸፈን አስፈላጊ ነው ብለዋል። ዛሬ የተመረቀው የኖህ ሳይት ለከተማችን ቤት ብቻ ሳይሆን ውበትም የሚጨምር ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

ኖህ ሪል ስቴት ባለፉት አስርት ዓመታት በ33 ሳይቶች ከ9,800 በላይ የመኖሪያ ቤቶችንና የንግድ ማዕከላትን ከ25,000 በላይ ለሚሆኑ ቤት ፈለጊዎች ገንብቶ ያስረከበ ድርጅት ነው።

Addis Admass

28 Oct, 12:13


ኖህ ሪል ስቴት ሰሚት ላይ የገነባቸውን 750 አፓርመንቶች ቪላ ቤቶችና የንግድ ሱቆች አስረከበ

"ኖህ ኤርፖርት ድራይቭ ሳይት" የሚል ስያሜ የተሰጠው በሰሚት አከባቢ የተገነባው አፓርትመንት በዛሬው ዕለት ለቤት ባለቤቶች የተላለፈ ሲሆን መኖሪያ ቤቶቹም ከ75 ካሬ እስከ 128 ካሬ ስፋት ያላቸው መሆናቸው በቤት ማስረከቢያ ስነ ስርዓቱ ላይ ተገልጿል። ቤቶቹ ከባለ 2 እስከ ባለ 3 መኝታ ክፍል ያሏቸው ብዛታቸው 750 በላይ አፓርታማ የመኖሪያ ቤቶች፣ ከ32 በላይ ቪላ ቤቶች እንዲሁም 45 የንግድ ሱቆች ናቸው።

Addis Admass

26 Oct, 21:01


https://t.ly/MwYTJ

Addis Admass

26 Oct, 20:57


https://t.ly/mWbX8

Addis Admass

26 Oct, 20:51


https://t.ly/oHQl7

Addis Admass

26 Oct, 20:48


https://t.ly/6KLyn

Addis Admass

26 Oct, 19:51


ውድ አንባቢያን

ሳምንታዊ የቅዳሜ ጋዜጣችሁን አዲስ አድማስን፣ በእነዚህ
የመዲናችን መፃሕፍት መደብሮች ውስጥ እንደምታገኙት
ልናስታውሳችሁ እንወዳለን፡፡
• ጃፋር መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ)
• ክብሩ መፃሕፍት መደብር (ጥቁር አንበሳ፣ ትራኮን ህንጻ)
• እነሆ መፃሕፍት መደብር (አራት ኪሎ)
• ኢዞጵ መፃሕፍት መደብር (አቡነ ጴጥሮስ)
• አምደ መፃሕፍት መደብር (ሜክሲኮ)

አዲስ አድማስ የእርስዎና ቤተሰብዎ

Addis Admass

26 Oct, 19:46


“በጥቅምት አንድ አጥንት” ነገም ይቀጥላል
ቢጂአይ ኢትዮጵያ አብዛኛውን ወጪ ሸፍኖለታል የተባለው የቤተሰብ ፌስቲቫል በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል እየተካሄደ ነው፡፡ “በጥቅምት አንድ አጥንት” በተሰኘው በዚህ ዓመታዊ የቤተሰብ ፌስቲቫል ላይ ጥሬ ስጋ በግማሽ ዋጋ እየተቆረጠ ሲሆን፤ ቢጂአይ ኢትዮጵያ ፌስቲቫሉ የሁሉንም አቅም ያገናዘበ ይሆን ዘንድ በተለይ የጥሬ ሥጋውን ግማሽ ዋጋ ሸፍኗል ተብሏል፡፡
“የዘንድሮውን ፌስቲቫል ግማሽ ወጪ የሸፈንነው ደንበኞቻችንን ስለምናከብር ነው” ብሏል - ኩባንያው፡፡
በሴንቸሪ ፕሮሞሽንና ኤቨንትስ የተዘጋጀው የቤተሰብ ፌስቲቫል፣ ዛሬ ጠዋት ረፋድ ላይ የተከፈተ ሲሆን፤ የከተማችን 10 ታዋቂ ሥጋ ቤቶች እየተካፈሉበት ነው፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ የቢጂአይ ምርቶች የሚቀርቡ ሲሆን፤ አንጋፋዎቹ ድምጻውያን አብነት ግርማና ፍቅር አዲስ ነቅአጥበብን ጨምሮ ሌሎችም ኹነቱን እንደሚያደምቁት ነው የተነገረው፡፡
ሴንቸሪ ፕሮሞሽንና ኤቨንትስ ፌስቲቫሉን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ፤ ህብረተሰቡ በአንድ ቦታ ተሰባስቦ፣ አብሮ የመብላትና የመጠጣት እንዲሁም የመዝናናትና የመመካከር ባህሉን የሚያጠናክርበት ነው ብሏል፡፡
“በጥቅምት አንድ አጥንት” በሚል የሚካሄደው የቤተሰብ ፌስቲቫል ነገም እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል፡፡

Addis Admass

26 Oct, 19:35


ሴት አባላት ሳይኖራቸው አለን በማለት ገንዘብ
የተቀበሉ ፓርቲዎች መታገዳቸው ተገለጸ


ሴት አባላት ሳይኖራቸው አለን በማለት፣ በሀሰተኛ ሪፖርት ገንዘብ የተቀበሉ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ማገዱን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።

የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ የሌላቸውን ሴት አባላት ቁጥር አለን በማለት የሃሰት ሪፖርት በማቅረብ ገንዘብ በመቀበል ህገ ወጥ ተግባር መፈጸማቸው መረጋገጡን ቦርዱ ጠቁሟል፡፡

የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ በቅርቡ በተሻሻለው የፓርቲዎች አገልግሎትና ምዝገባ ክፍያ እንዲሁም እገዳ በተጣለባቸው ፓርቲዎች ዙሪያ በዛሬው ዕለት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ውብሸት በመግለጫቸው፤ ቦርዱ በፓርቲዎች ውስጥ የሚሳተፉ ሴቶችንና አካል ጉዳተኞችን ለማበረታታት ለፓርቲዎች ገንዘብ የሚሰጥበት አሰራር መዘርጋቱን ገልጸዋል።

ሆኖም ለማበረታቻ ከቦርዱ የሚመደበውን ገንዘብ አላግባብ ለመጠቀም፣ የሌላቸውን አባላት ቁጥር አለን በማለት የሚያቀርቡ ፓርቲዎች መኖራቸውን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡

ቦርዱ ባደረገው ማጣራት፤ የጋምቤላ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣ አገው ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ፣ አዲስ ትውልድ ፓርቲ፣ የወላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ ፓርቲ የሌላቸውን ሴት አባላት ቁጥር አለን በማለት የሃሰት ሪፖርት በማቅረብ ገንዘብ በመቀበል፣ ህገ ወጥ ተግባር በመፈጸማቸው የዕግድ ውሳኔ እንደተላለፈባቸው አብራርተዋል።

ተመሳሳይ ችግር ያለባቸው ሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎችም ላይ እርምጃ መውሰዱን አቶ ውብሸት ገልጸዋል።

Addis Admass

26 Oct, 19:35


የአዲስ አድማስ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ
=====
አዲስ አድማስ https://bit.ly/2V1zyZQ
ፌስቡክ↠ https://bit.ly/2V0I6jx
ትዊተር↠ https://bit.ly/33fDhaP
ቴሌግራም↠ https://bit.ly/2JgeCvG
ዩቲዩብ ↠ https://bit.ly/3q2hXiv

Addis Admass

26 Oct, 19:35


ኢትዮጵያ በብሪክስ ጉባኤ በሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ሚዛናዊ አቋም አሳይታለች - በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር
**********************

ኢትዮጵያ በብሪክስ ጉባኤ በሀገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ያላትን ሚዛናዊ አቋም በግልጽ ማሳየቷን በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴሬክሂን ተናግረዋል፡፡

አምባሳደሩ ሀገሪቱ በጉባኤው ላይ ብሔራዊ ጥቅሟን የሚያስጠብቁ ኃሳቦችን ማንጸባረቋን ገልጸዋል፡፡

ኢትዮጵያ በብሪክስ ያላት ተሳትፎ ለጋራ ዕድገት አዎንታዊ ሚና እንደሚጫወትም አምባሳደር ኤቭጌኒ ቴሬክሂን ጠቁመዋል፡፡

የሀገሪቱ የብሪክስ ተሳትፎ ከምጣኔ ኃብታዊ ዕድገት ባሻገር ለህብረቱ ዓላማ መሳካት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም መናገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ከሰሞኑ በሩሲያ ካዛን ከተማ የተካሄደው 16 ኛው የብሪክስ ጉባኤ ፍትኃዊ የዓለም ሥርዓት መፍጠር የሚያስችሉ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

Addis Admass

26 Oct, 19:12


27ቱ ለብልፅግና ፓርቲ አመራሮች የቀረቡ ጥያቄዎች


ገዢው ፓርቲ ብልጽግና፤ “የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት” በሚል ርዕስ ለፓርቲው አመራሮች ሦስተኛውን ዙር ሥልጠና በመላ አገሪቱ እየሰጠ ሲሆን፤ ሠልጣኞች 27 ጥያቄዎችን በግላቸው አቅም ብቻ እንዲመልሱ እየተደረገ ነው ተብሏል፡፡

በአዲስ አበባ ከሳምንት በፊት ለ10 ቀናት ስልጠናውን የወሰዱ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በርከት ያሉ ጥያቄዎችን በግላቸው አቅም ብቻ ሰርተው እንዲመልሱ መደረጉ ተጠቁሟል፡፡

ካለፈው ሳምንት ሰኞ የተጀመረውና ለ11 ቀናት ይቆያል በተባለው ሦስተኛው ዙር ስልጠና እየተሳተፉ የሚገኙ የፓርቲው አመራሮችም፣ ሃያ ሰባቱን ጥያቄዎች እርስ በእርስ ሳይመካከሩ መመለስ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ለሰልጣኞቹ በተዘጋጀው የጥያቄ ወረቀት ላይ ከሰፈሩ ጥያቄዎቹ መካከል፤ “የዳቦ ጥያቄ እያለ የኮሪደር ልማት ለምን መስራት አስፈለገ?” ለሚል ጥያቄ ምን ምላሽ ትሰጣላችሁ? የሚል ይገኝበታል።

በተጨማሪም ጥያቄዎቹ፣ የኮሪደር ልማት እንዲሁም የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማሻሻያ ለምን እንዳስፈለገ፣ የአብዮታዊ ዲሞክራሲና የመደመር ቁልፍ ልዩነቶችን ምን እንደኾኑ፣ የሰላም እጦት ቁልፍ ምክንያቶችን፣ ሰላምን ለማረጋገጥ የተደረጉ ጥረቶችንና ተግዳሮቶችን እንዲሁም ውጭ ጉዳይና ብሄራዊ ትርክትን ማብራራትን ይጨምራሉ።

ለሰልጣኞቹ የቀረቡላቸው ጥያቄዎች ከዚህ በታች ቀርበዋል፡፡

የአመራር ምዘና ጥያቄዎች
1. አንድ ሰው ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ችግሮች እያሉ ወይም የዳቦ ጥያቄ ሳይመለስ ለምን የኮሪደር ልማት ትሰራላችሁ ቢል ምላሻችን ምንድነው? የኮሪደር ልማት መፍጠር ለምንፈልገው ኢኮኖሚና ማሳካት ለምንፈልገው ማህበራዊ ግብ ያለው ዋጋ ምንድነው?
2. የብልፅግና ማዕከልነት ምንድነው? ከፖለቲካ፣ ከኢኮኖሚና ከውጭ ጉዳይ አንጻር የሀሳብ መነሻዎችንና ተግባራዊ ምሳሌዎችን በመጥቀስ አስረዱ? ከትርክት አንጻር በመዳሰስ አስረዱ?
3. አገልጋይነት ስነ-ምግባራዊ አመራር የሚያደርገው ምንድነው? አገልጋይነት ከሌሎች አመራር ዘዴዎች የተለየ የሚያደርገው ምንድነው? አገልጋይ መሪነት ለብልፅግና ተመራጭ የሚሆነው ለምንድነው?
4. የመደመር መሰረታዊ እሳቤ ከብሔራዊነት ትርክትና ከህልማችን ጋር ያለው ትስስር ምንድነው? የብሔራዊነት ትርክትና የሀገራዊ ህልም ትስስር ምንድነው?
5. ህልውና መር አካሄድን ከሀገራችን ታሪክ ጋር በማያያዝ አስረዱ? ያመጣው ውጤትና የፈጠረው ውድቀት ምንድነው?
6. ብልፅግና የእይታ እና የምናብ ለውጥ ነው፡፡ ይህንን የእይታ ለውጥ ከታሪክ ምልከታ እና እጣፈንታችን ከመወሰን አንጻር አስረዱ?
7. የተለያዩ የተሰሩ ስራዎችና ኢንሼቲቮች መነሻ ህልም እና የሚፈጥሩት አለም እና አቅም ምንድናቸው?
8. ሳይንስ ሙዚየም፣ አብርሆት፣ ገበታ ፕሮጀክቶች ከፍ ያለ ምናብ እና አርቆ እይታ ውጤቶች ናቸው ሲባል ምን ማለት ነው? ህልማችንን ልዕልና መር የሚያደርገው ምንድነው? የህልማችን መዳረሻ እና ተግባራዊ ምሳሌዎችን በማገናኘት አስረዱ?
9. የፖለቲካ ገበያ የጋራ ህልማችን እንቅፋት ነው ሲባል ምን ለማለት ነው?
10. በነባራዊና አለም አቀፋዊ ትንታኔያችን ውስጥ ብዝሀ ቀውስ፣ የመረብ ዘመን እና ድህረ-እውነት የሚሉ ጉዳዮችን ደጋግመን እንገልጻለን፡፡ እነዚህ ጉዳዮች በማያያዝ እና በማሰናሰል ነባራዊ አለም አቀፍ ሁኔታ ምልከታችንን አስረዱ? እነዚህ እውነታዎች ከሀገራችን ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና ዲፕሎማሲ አንጻር እየፈጠሩ ያሉትን እና የሚኖረውን አወንታዊ እና አሉታዊ ተጽዕኖ አስረዱ?
11. የስነ-ምግባር አስተውሎት/ኢንተለጀንስ ለአመራሩ ቁልፍ የሚያደርገው ምንድነው? ብልፅግናን ለማረጋገጥ እና ለመደመር ስነ-ምግባር አስፈላጊ ነው ቢባል ምን ለማለት ነው?
12. የለውጥ ዋና ዋና ስኬት ከሆኑት ውስጥ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና በውጭ ግንኙነት ውጤቶች አንዳንድ በመዘርዘር ከእነዚህ ውጤቶች ጀርባ ያለውን የሀሳብ መነሻ እና የአካሄድና የመንገድ ልዩነት አስረዱ?
13. የህግ ማስከበር ተቋማት ሪፎርም በተቋማት ውስጥ እና በሀገር ግንባታ ውስጥ የፈጠረው ለውጥ እና ያመጣውና የሚያመጣው ተጽዕኖ ምንድነው?
14. የተቋማት ግንባታ የለውጡ መሰረታዊና ቁልፍ ጉዳይ የሆነው ለምንድነው? አመራሩ በተቋማት ግንባታ ውስጥ የሚጫወተው ሚና ምንድነው?
15. የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎቻችን ከህልማችን መዳረሻ እና ስኬት ጋር በማያያዝ አስረዱ?
16. ህልውና መር እይታ ከችግር የማያሻግር የተባለበት ምክንያት ምንድነው?
17. የሀገራዊ ህልማችን ቁልፍ መዳረሻዎች ምንድናቸው? በዝርዝር አስረዱ?ህልምን ለማሳካት እንቅፋቶች ምንድናቸው? ህልምን ለማሳካት ከአመራሩ ምን ይጠበቃል?
18. የፖለቲካ ሪፎርም ማድረግ ለምን አስፈለገ? የፖለቲካ ሪፎርም ገፊ ምክንያቶች፡-የፖለቲካ ሪፎርም ማድረግ ያስፈለገበት ምክንያት፡-የሪፎርሙ መሰረቶች ምንድናቸው? ውጤታማነቱስ እንዴት ይመዘናል? የፖለቲካ ሪፎርም ውጤታማነት መመዘኛዎች፡-የመሃል ፖለቲካን ባህሪያትና ፋይዳ ተረድቶ የመምራት አስፈላጊነትን አስረዱ? የጠንካራ ፓርቲ ግባችንን ማሳካት ለህልማችን እውን መሆን ያለውን ፋይዳ አስረዱ? የጠንካራ ፓርቲ ግባችንን ማሳካት ለህልማችን እውን መሆን ያለውን ፋይዳ፡-ፓርቲያችንን ለማጠናከር ከአመራሩ ምን ይጠበቃል?
19. የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረግ ለምን አስፈለገ? የሪፎርሙ አንጓዎች ምንድናቸው? ምን አይነት ውጤትስ ያመጣል?
20. አብዮታዊ ዲሞክራሲ እና መደመር ቁልፍ ልዩነቶችን አስረዱ? በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በውጪ ግንኙነት የምንከተላቸው መንገዶች ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ ጋር ያለውን ልዩነት በዝርዝር አስረዱ?
21. የሰላም እጦት ቁልፍ ምክንያቶች ምንድናቸው? የብልጽግና የሰላም ግንባታ ግብ ምንድነው? ሰላምን ለማምጣት የምንከተለው አካሄድ ከነባሩና ከተለመደው አካሄድ ጋር ያለው ልዩነት ምንድነው? ሰላምን ለማረጋገጥ ያደረግናቸው ጥረቶች እና የመጡት ውጤቶች ምንድናቸው? የገጠሙን ተግዳሮቶችስ?
22. ከለውጡ በኋላ ብዙ ኢንሼቲቮች ተጀምረው ውጤት አምጥተዋል፡፡ ከእነዚህ ኢንሼቲቮች ጀርባ ያለው ሀሳብ፣ የተሰሩበት መንገድ፣ የሚያመጡት ውጤት ምን ለመድረስ እና ለመፍጠር በማመን ነው? ከሀሳቦቻችን ጋር በማስተሳሰር አስረዱ? እየፈጠሩት ያለው የአመለካከት እና የባህል ለውጥ አስረዱ?
23. የምግብ ሉዓላዊነት የብልጽግና ቁልፍ አጀንዳ ሆነ? የምግብ ሉዓላዊነት ግቦቻችን ምንድናቸው? የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ዋና ዋና ስራዎች ምንድናቸው? ያመጡት ውጤትስ?
24. የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ያለውን ቁልፍ ሀገራዊ ፋይዳ አብራሩ? ከኢኮኖሚ፣ ከፖለቲካ፣ ከተቋማት መፈጸም ብቃት እና ከዲፕሎማሲ አንጻር?

Addis Admass

26 Oct, 19:12


25. የለውጡ የውጭ ግንኙነት ዋነኛ የአመለካከት እና የተግባር ልዩነት ምንድነው? ዘላቂ ወዳጅነት የመሰረትንባቸው ሀገራት እነማን ናቸው? 26. ለስኬት እያበቁን ያሉ ቁልፍ የአመራርነት ሚናዎች ምንድናቸው? በሀገራችን ቁልፍ የአመራር ክፍተቶች እና ውድቀቶች ምንድናቸው? በተለይም ለችግር እየዳረጉን ያሉ ቁልፍ የአመራር ክፍተቶች ምንድናቸው? በአመራር ክፍተት ምክንያት የተፈጠሩ ወይም የተባባሱ ቁልፍ ሀገራዊ ችግሮች ምንድናቸው? እንደ ብልጽግና አመራር ካለፈው መማር እና ማዳበር ያለብን ቁልፍ የአመራርነት ክህሎቶች ምንድናቸው? አንድ አመራር የብልጽግና አመራር የሚሆነው ምን ሲሆን ነው? ፓርቲያችን የአመራርን ክፍተት ለማረም እየተከተለው ያለው ስትራቴጂ ምንድነው? ምን ይጎድለዋል? ምን ይታረም?
27. ከዚህ አመራር የቀሰሙትን እውቀት እና ያገኙትን ውጤት ከሚመሩት ተቋም፣ ከሚመሩት ክልል፣ ዞን ጋር በማስተሳሰር በዝርዝር አስረዱ? ከስልጠናው ተነስተው ቀጣይ ግለሰባዊ እቅድ እና ተቋማዊ እና አስተዳደራዊ እቅድ በዝርዝር ያስቀምጡ?
(ምንጭ፡- ዋዜማ ሬዲዮ)

Addis Admass

26 Oct, 12:42


"በጥቅምት አንድ አጥንት" በኤግዚብሽ ማዕከል ተከፈተ - ጥሬ ስጋ በግማሽ ዋጋ እየተሸጠ ነው

Addis Admass

25 Oct, 18:42


🟠 በማለዳ ይጠብቁን!! 🟠

Addis Admass

22 Oct, 19:52


ኤስ ኦ ኤስ በአገር ውስጥ ገንዘብ በማሰባሰብ ራሱን የማስተዳደር ዕቅድ እንዳለው ገለጸ

ኤስ ኦ ኤስ የሕጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ በጀቱን ከውጭ ለጋሾች ሳያመጣ በአገር ውስጥ በሚያሰባስበው ገንዘብ ራሱን የማስተዳደር ዕቅድ እንዳለው ገልጿል። ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ድርጅቱ በኢትዮጵያ ስራ የጀመረበትን 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል የማጠናቀቂያ መርሃ ግብር በሸራተን አዲስ ሆቴል አካሂዷል።

በዚሁ መርሃ ግብር ላይ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የኤስ ኦ ኤስ የሕጻናት መንደሮች ምስራቃዊና ደቡባዊ አፍሪካ ክልል ምክትል ዳይሬክተር አቶ በድሉ ሸገን የዓለም አቀፉን ኤስ ኦ ኤስ የሕጻናት መንደሮች ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንትን እንዲሁም የራሳቸውን መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በንግግራቸውም ድርጅቱን “ኤስ ኦ ኤስ የሕጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ በተደራሽ ቁጥርም ሆነ በፕሮግራም አፈፃፀም የተዋጣለት ስራ በመስራት በምስራቃዊና ደቡባዊ አፍሪካ ክልል ውስጥ ካሉት የኤስ ኦ ኤስ ፕሮግራሞች መካከል የመሪነቱን ስፍራ ይዞ የዘለቀ ጠንካራ ድርጅት” ሲሉ ገልጸውታል።

በዚሁ መግለጫ ላይ በአስር ዓመት ውሰጥ “በጀቴን ከውጭ አገር ሳላመጣ፣ አዚሁ በአገር ውስጥ ገንዘብ አሰባስቤ ራሴን በራሴ የማስተዳደር ዕቅድ አለኝ” ብሏል፣ ኤስ ኦ ኤስ።

Addis Admass

22 Oct, 19:52


የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ በተወካያቸው በኩል ባሰተላለፉት መልዕክት የድርጀቱን 50 ዓመታት ጉዞ አድንቀው፣ ይህ ጠንካራ የልማት አጋርነት በቀጣይም የበለጠ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

የኤስ ኦ ኤስ ስዊዘርላንድ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሚስተር አሌክስ ደ ጊዩስ በበኩላቸው፣ ድርጅታቸው ከዚህ በፊት የገንዘብ እንዲሁም የቴክኒክ ድጋፍ እንዳበረከተ አስታውሰው፣ ይህም ትብብርና ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።
የኤስ ኦ ኤስ የሕጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ በ50 ዓመታት የበጎ ተጽዕኖ ጉዞው 8 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሰዎችን መድረስ እንደቻለ Global Exceptional Excellence Consultancy የተባለው ድርጅት ያደረገው ጥናት ያመለክታል።

ኤስ ኦ ኤስ የሕጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች ፌዴሬሽን ብሔራዊ አባል የሆነ በሕጻናት ደሕንነት ጥበቃና ልማት ላይ አተኩሮ የሚሰራ ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት ነው፡፡

Addis Admass

22 Oct, 19:35


"መንታ ፍቅር"፤ ከጥቅምት 28 ጀምሮ በአለም ሲኒማ!

ለቁጥር የሚያዳግቱ ፊልሞችን የሰራው የጥበብ ሰው የቢንያም ወርቁ፣ በ”ቼበለው“ ፊልሙና በጥናታዊ ፊልሞቹ የሚታወቀው የዳንኤል ወርቁ እና እጅግ ተወዳጅ የነበረው ”ቫኬሽን ፍሮም አሜሪካ“ን ፊልም ፅፎ፣ ድንቅ ትወናውን ያሳየው የዮናዳብ ወርቁ ታናሽ ወንድም ዮናታን ወርቁ (ሻንቄ)፣ የወንድሞቹን ፈለግ በመከተል አሳዛኝ፣ አስደማሚ፣ አስቂኝ ጭምር የሆነ "መንታ ፍቅር" ግራ የተጋቡ ነፍሳት የተሰኘ ድንቅ ፊልም ይዞ ብቅ ብሏል።

ፊልሙ፤ ሰለሞን ቦጋለ ድንቅ አድርጎ የተወነበት ሲሆን፣ አዩ ግርማ አቅሟን አሳይታበታለች፡፡ በተጨማሪም፣ ራሱ ዮናታን ወርቁ፣ በ“ቫኬሽን” ላይ ተወዳጅ የነበረው ዮናዳብ ወርቁ፣ በብዙ ፊልሞች ላይ ብቃቷን ያሳየችው ቤተልሄም ከፍ ያለው፣ የ“አየር ላይ ነን” ሲትኮም ተወዳጅዋ ሙሉነሽ ተሰማ፣ ሲሳይ በቀለ፣ ያሬድ ኤጉና ሌሎችም ታዋቂና ወጣት ተዋንያን የተሳተፉበት ነው። "መንታ ፍቅር"፤ ከጥቅምት 28 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአለም ሲኒማ መታየት ይጀምራል። ሊያመልጣችሁ የማይገባ ፊልም ነው፡፡

Addis Admass

22 Oct, 19:04


ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የአገልግሎት
ክፍያ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ አደረገ

• በአዲሱ የክፍያ ተመን ፓርቲዎች ከ5ሺ ብር - 15ሺ ብር ይከፍላሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የሰነድ ማሻሻያ አገልግሎት ክፍያ ላይ ከፍተኛ ጭማሪ አደረገ፡፡ ፓርቲዎች ጊዜያዊ ሰርተፊኬት ወይም ዕውቅና ለማግኘት ይከፍሉት የነበረው 100 ብር የአገልግሎት ክፍያ ወደ 15 ሺ ብር አሻቅቧል፡፡

ቦርዱ የክፍያ ማሻሻያ ተመን ያደረገው የጊዜያዊ ዕውቅና፣ የሙሉ ዕውቅና እና የሰነድ ማሻሻያ ክፍያ ላይ መሆኑን ዛሬ ጥቅምት 12 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡

እስካሁን የፖለቲካ ፓርቲዎች ጊዜያዊ ሰርተፊኬት ለማግኘት 100 ብር፣ ለሙሉ ዕውቅና 200 ብር እንዲሁም ሰነዶቻቸውን በጉባኤ አሻሽለው ሲያቀርቡ 30 ብር የአገልግሎት ክፍያ ሲከፍሉ መቆየታቸውን ያስታወሰው ቦርዱ፤”ይህን የክፍያ መጠን በየጊዜው ማሻሻል እንደሚያስፈልግ በማመን፣” አዲሱን የአገልግሎት ክፍያ ተመን መወሰኑን አመልክቷል፡፡

ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው የተሻሻለ የክፍያ ተመን መሰረት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጊዜያዊ ሰርተፊኬት ለማግኘት 15 ሺ ብር፣ ለሙሉ ዕውቅና 30 ሺ ብር እንዲሁም ለሰነድ ማሻሻያ 5 ሺ ብር መክፈል ይጠበቅባቸዋል፡፡

የተሻሻለው የአገልግሎት የክፍያ ተመን ከጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን ቦርዱ አስታውቋል፡፡

Addis Admass

22 Oct, 18:47


“ዳናሽ” የፍቅር ፊልም በመጪው ማክሰኞ ይመረቃል

3 ሚሊዮን ብር እንደፈጀ የተነገረለት “ዳናሽ” የተሰኘ የፍቅር ፊልም፣ በመጪው ማክሰኞ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ከቀኑ በ11፡30 በዓለም ሲኒማ፣ በቀይ ምንጣፍ ሥነስርዓት እንደሚመረቅ ተገለጸ፡፡

የአብርሃም ታደሰ ሥራ የሆነው “ዳናሽ”፤ በኢነርጂ ፊልም ፕሮዳክሽንና በቆንጆ ፊልም ፕሮዳክሽን ተዘጋጅቶ፣ በየሚ ፊልም ፕሮዳክሽን የቀረበ ነው ተብሏል፡፡

በዛሬው ዕለት ጠዋት ረፋዱ ላይ የፊልሙ ደራሲና ዳይሬክተር አብርሃም ታደሰ፣ የፊልም ፕሮዳክሽን ባለቤቶቹና ሦስት ዋና ተዋናዮች በፊልሙ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በቫይብስ ሆቴል በተሰጠው የጋራ መግለጫ ላይ እንደተነገረው፣ የፊልሙ ዘውግ የፍቅር ድራማ ሲሆን፤ የ1፡46 ደቂቃ ርዝማኔ አለው፡፡ መቼቱን አዲስ አበባ ላይ ያደረገው “ዳናሽ” ፊልም፤ ከቅድመ ዝግጅት አንስቶ እስከሚጠናቀቅ ድረስ ሁለት ዓመት ፈጅቷል ተብሏል፡፡

የፊልሙ ደራሲና ዳይሬክተር እንደገለጸው፤ የፊልሙ ጭብጥ በፍቅር፣ ታማኝነትና መስዋዕትነት ዙሪያ የሚያጠነጥን ነው፡፡ በፊልሙ ላይ በአጠቃላይ 95 አንጋፋና ወጣት ተዋናዮች እንደተሳተፉበትም ተናግሯል፡፡

ለፊልሙ ደራሲና ዳይሬክተር አብርሃም ታደሰ “ዳናሽ” የበኩር ሥራው ሲሆን፤ የዛሬ ሳምንት ማክሰኞ በዓለም ሲኒማ በደማቅ ሥነስርዓት ከተመረቀ በኋላ፣ ከጥቅምት 22 አንስቶ በሁሉም ሲኒማ ቤቶች መታየት ይጀምራል፡፡

Addis Admass

21 Oct, 20:34


መርካቶ ሸማ ተራ አካባቢ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል::
የ እሳት አደጋዉን በቁጥጥር ስር በማዋል ርብርብ ያደረጋችሁ ፤ በርካታ ሎጀስክ በማቅረብ የደገፋችሁን እና ከዚህ በላይ ሊደርስ የነበረዉን ጉዳት የቀነሳችሁ አካላትን በሙሉ በራሴ እና በከተማ አስተዳደሩ ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ::
በንብረት ላይ የደረሰው ጉዳት ያሳዝናል። መንስኤዉን በማጣራት የምናሳዉቅ ሲሆን ህብረተሰቡ ሁሌም መሰል አደጋዎች እንዳይከሰቱ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እዲያደግ አደራ እላለሁ። ከንቲባ አዳነች አቤቤ

Addis Admass

21 Oct, 20:03


በመርካቶ ሸማ ተራ አከባቢ የተከሰተውን የእሳት አደጋ እስከ አሁን መቆጣጠር ባለመቻሉ አሁንም ድረስ የአደጋ መከላከል ሰራተኞች በሄሊኮፕተር በመታገዝ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ይገኛል ።

Addis Admass

21 Oct, 19:52


በዚህ ውድድር ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ግለሰቦች ወይም ድርጅቶች፣ ራሳቸው ወይም ጠቋሚዎች፣ በቴሌግራም ቻናል:-@ BIWPrize ወይም በኢሜይል፡[email protected] በመጠቀም ለሰላምና ኢኮኖሚ ያበረከቷቸውን ሥራዎች ከዛሬ ጥቅምት 11 ቀን ጀምሮ ለቀጣይ 15 ቀናት መላክ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡


ለዚህ ሽልማት እጩ ለመሆን ተወዳዳሪዎች ማሟላት የሚገባቸው ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፡-

ለኢኮኖሚ ሽልማት ዘርፍ
1. ከትንሽ ተነስቶ በራሱ ጥረት የተሻለ ደረጃ ላይ መድረስ የቻለ
2. ለብዙዎች የሥራ በር የከፈተ
3. በሥራ ፈጠራ የተካነ
4. ህዝብና አገርን ለመጥቀም የሚሰራ
5. ካፈራው ሃብት ማህበራዊ ሃላፊነቱን የሚወጣ
6. በሥራ ትጋቱ ለብዙዎች ምሳሌ የሚሆን
7. እውቀቱንና ልምዱን ለትውልድ ለማካፈል የማይሰስት
8. የአረንጓዴ ልማት አስፈላጊነትን በደንብ የተረዳ
9. የዲጂታል ኢኮኖሚን ጥቅም የሚያውቅ


ለሰላም ሽልማት ዘርፍ
1. በአመለካከቱ፣ በንግግሩ፣ በአኗኗሩ ሰላምን ከፍ የሚያደርግ
2. ለሰብአዊ መብት መከበር ግድ የሚለው
3. ዋጋ ከፍሎ በህብረተሰብ መካከል እርቅን ለማውረድ የሰራ
4. ይቅርታን እየኖረ፣ ይቅርታን የሰበከ
5. የሃይል አማራጭን የማያደፋፍር
6. ለሃገርና ለወገን ሰላም እንደ ግል ህይወቱ ትኩረት የሚሰጥ
7. መልካም አስተዳደርን የሚያበረታታና ለድሆች መብት የሚሟገት
8. ቀና አመለካከትን የሰበከ
9. የጾታ እኩልነትን ያበሰረና ጥቃትን የሚጸየፍ

Addis Admass

21 Oct, 19:51


አንቴክስ ኢትዮጵያ ላለፉት 7 ዓመታት በአገሪቱ ውስጥ በነበረው ቆይታ፣ ያሉትን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ውጣ ውረዶች በመገንዘብ፣ መፍትሄ የማፈላለግ ሂደት ውስጥ የራሱን ሚና ለመወጣት ባቋቋመው ፉድ ኤንድ ፕላስ የተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት አማካኝነት በርካታ እርዳታዎች ሲያደርግ መቆየቱ በመግለጫው ላይ ተጠቁሟል፡፡


በአሁኑ ወቅት ደግሞ የዚሁ አካል የሆነ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማትና ሰላም የላቀ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶች ዕውቅና የሚሰጥ ምርጥ ተጽዕኖ ፈጣሪ ሥራዎች (Best Influencer Work Prize)ሽልማትን ለመስጠት እየተንቀሳቀሰ ሲሆን፤ ከዛሬ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም አንስቶ የእጩ ተወዳዳሪዎችን ታሪኮችና ሥራዎች መቀበል እንደጀመረ ተነግሯል፡፡


የBIW Prize ዓላማ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማምጣት በተለየ መንገድ ጥረት ለሚያደርጉና በህዝቡ መካከል ሰላማዊ አብሮነትን ለማጎልበት ለሚተጉ፣ በሥራቸውም ለሌሎች አርአያ መሆን የቻሉ ግለሰቦችና ድርጅቶችን ማበረታታትና ሥራቸውንም ማገዝ ነው፤ተብሏል፡፡


አንቴክስ ኢትዮጵያ በአዳማ ኢንዱስትርያል ፓርክ ከ10 በላይ ሼዶች ያሉት ሲሆን፤ ለ4500 ሰራተኞች የሥራ ዕድል የፈጠረ ድርጅት መሆኑ ተነግሯል፡፡ አንቴክስ ግሩፕ፤ እ.ኤ.አ በ2003 ዓ.ም በቻይና የተመሰረተ ሲሆን፣ ከቻይና በተጨማሪ በእስያና በአፍሪካ በጨርቃጨርቅና ሌሎች ዘርፎች እየሰራ የሚገኝ ድርጅት ነው፡፡

Addis Admass

21 Oct, 19:50


አንቴክስ ጨርቃጨርቅ ኃ.የተ.የግ.ማ. የ20 ሚ. ብር ውድድር አዘጋጀ

• በኢኮኖሚና በሰላም ዘርፍ ያሸነፉ 2 ተወዳዳሪዎች በነፍስ ወከፍ 10 ሚ. ብር ይሸለማሉ

• የሽልማት ሥነስርዓቱ ታህሳስ 17 በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ይካሄዳል

ላለፉት 7 ዓመታት በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ በጨርቃጨርቅ ምርት ላይ የተሰማራው የቻይናው አንቴክስ ጨርቃጨርቅ ኃ.የተ.የግ.ማ፤ ለኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ልማትና ሰላም የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶችን አወዳድሮ 20 ሚሊዮን ብር ሊሸልም መሆኑ ተገለጸ፡፡


የአንቴክስ ኢትዮጵያ አመራሮችና ዝግጅቱን የሚያስተባብረው በሻቱ ቶለማርያም መልቲሚዲያ፣ ዛሬ ተሲያት በኋላ፣ በአዳማ ኢንዱስትሪያል ፓርክ የድርጅቱ አዳራሽ በሽልማቱ ዙሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

በመግለጫው ላይ እንደተብራራው፣ ድርጅቱ በኢኮኖሚ ልማትና በሰላም ዘርፍ የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦችና ድርጅቶችን አወዳድሮ ያሸነፉ ሁለት ግለሰቦች ወይም ድርጅቶችን ለእያንዳንዳቸው 10 ሚሊዮን ብር ይሸልማል፡፡


ለዚህ ሁለት የሽልማት ዘርፎች የሚመረጡ እጩዎች ከመላው ኢትዮጵያ በህዝብ ጥቆማ ታሪካቸው ወይም ሥራቸው እንደሚሰበሰብ የተጠቆመ ሲሆን፤ አሸናፊዎች ለዚህ ውድድር በተመረጡ ዳኞችና በህዝብ ድምጽ ተለይተው የሽልማት ሥነስርዓቱ ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም በአፍሪካ ህብረት የስብሰባ ማዕከል እንደሚካሄድ ታውቋል፡፡

Addis Admass

21 Oct, 19:42


አዲሱ የመንግሥት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ስኬል ይፋ ተደረገ

መንግሥት በዛሬው ዕለት አዲስ የሠራተኞች ደሞዝ ጭማሪ ስኬል ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ የመንግሥት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪውን ከጥቅምር ወር ጀምሮ ያገኛሉ ተብሏል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ባለፈው ነሃሴ አጋማሽ ላይ 2.4 ሚሊዮን ገደማ ለሚሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ከ5% እስከ 332% የሚደርስ የደሞዝ ጭማሪ ሃሳብ ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ ለዚህም የ91.4 ቢሊዮን ብር ተጨማሪ በጀት እንደሚያስፈልግ አስታውቋል፡፡

የመንግሥት ሠራተኞች የደሞዝ ጭማሪው ባለፈው ሃምሌ ወር አገሪቱ የተገበረችውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የሚከሰቱ የኑሮ ውድነት ጫናዎችን ሠራተኛው መቋቋም እንዲችል ታልሞ የተደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡

አዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ማሻሻያ ስኬል ከዚህ በታች ቀርቧል፡፡

Addis Admass

21 Oct, 19:39


በፍኖተ ጽድቅ ማኅበር መሥራች መጋቤ አእላፍ ጸጋዬ ደበበ ሙሉ ወጪ የተገነባው ይኸው ስቱዲዮ፤ ድርጅቱ በሚያሰራጫቸው ይዘቶች የፕሮዳክሽን ጥራት ለመጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል፡፡

የቴሌቪዥን ተቋሙ በቅርቡ ከሰሜን አሜሪካ አህጉረ ስብከት ኅብረት በተደረገለት ድጋፍ የቀጥታ ሥርጭት የጀመረ ሲሆን፤ በሣተላይት በኢትዮ ሳት እና በዲኤስ ቲቪ እንዲሁም በዲጂታል ሚዲያ ሥርጭቱን ይበልጥ በማሳደግ ላይ ይገኛል ተብሏል።

Addis Admass

21 Oct, 19:38


”ፍኖተ ጽድቅ“ ያስገነባው ዘመናዊ ስቱዲዮና
50 ሚ. ብር የሚያወጣ ስክሪን ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን መገናኛ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት የተገነባው አዲስ ዘመናዊ ስቱዲዮና 50 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ስክሪን ተመርቋል፡፡

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በማኅበራት ምዝገባና ቁጥጥር መምሪያ እውቅና የተሰጠው "ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር"፣ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን ሥርጭት ድርጅት ያስገነባው ዘመናዊ ስቱዲዮ ባለፈው ቅዳሜ ጠዋት በታላቅ ድምቀት ተመርቋል።

አዲሱ ስቱዲዮ አንድ ዘመናዊ ስቱዲዮ ማሟላት የሚገባውን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማሟላቱ የተነገረ ሲሆን፤ስቱዲዮው ግዙፍ 8k ስክሪን የተገጠመለትና የተለያዩ ቀረጻዎችን ማከናወን የሚያስችሉ ገጽታዎችና የግንኙነት ካሜራ የተገጠመለት የስቱዲዮ መቆጣጠሪያ ክፍል እንዳለው ታውቋል፡፡

የስቱዲዮ ግንባታው ከ3 ዓመታት በላይ መፍጀቱ በምረቃው ሥነስርዓት ላይ ተገልጿል።

በምረቃው መርሐግብር ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የባሕርዳና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እንዲሁም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡