ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala @tariknwedehuala Channel on Telegram

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

@tariknwedehuala


የኢትዮጵያ ታሪኮች የሚቀርብበትና የሚዳሰስበት ቻናል

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala (Amharic)

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala በስልክ መሰናዶች ላይ የተገኘው ቻናል ነው። እንዴት እንዳለው ታሪኩን ለመመልከትና ማንበብ እንዴት እንደሚችሉ የሚረዳት መልእክት ለማድረግ ስብስቦን ይከተላቸዋል። ይህ ቻናል በኢትዮጵያ ታሪኩን በሚቀርብበትና የሚዳሰስበት፣ እና በሚስጥር አስራጭና ታማኝ ቻናሎችን ለማዘጋጀት እና ለማስታወቂያ ሊኖራቸው እንችላለን። በስልክ መሰናዶች እንቅስቃሴም ቻናሎች እንደሚፈታ እና እንደሚስራርም ቻናልን ስብስቡን ከእኛ እንደምንላክ ክፍል አለው።

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Feb, 18:51


ከላይ በምስሉ ላይ የሚታዩት የየካቲት ፲፪ የሰማዕታት ሐውልትን የቀረጹት ሁሉቱ የክሮኤሽያ (የያኔው ዩጎዝላቪያ) ዜጎች ሲሆኑ Antun Augustinčić እና Frano Kršinić ይባላሉ።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Feb, 17:58


ጀግናው የታክሲ ሹፌር ስምኦን አደፍርስ
(1905 -- 1929)

በእጅጉ አስገራሚ ታሪክ ነው። አስገራሚ ያልኩት በብዙ ምክንያት ነው። አንደኛው ኢትዮጵያ ውስጥ የታክሲ ስራ መቼ ተጀመረ ብለን ብንጠይቅ በ 1920ዎቹ ነው የሚል መልስ እናገኛለን። በ 1928 ዓ.ም አዲስ አበባ ውስጥ ስምንት ታክሲዎች ብቻ ነበሩ።

ከነዚህ የስምንቱ ታክሲዎች አንደኛው ባለቤት ስምኦን አደፍርስ ይባላል። የያኔው ዘመናዊ ሰው። መኪና ሲነዳ እንደ ብርቅ እና ተአምር የሚታይ ነበር። ከተለያዩ የታሪክ መዛግብት ያገኘሁትን የዚህን ጀግና ኢትዮጵያዊ ታሪክ እንኮምኩመው፡፡

ስምኦን አደፍርስ ፣ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ግራዚያኒ ላይ የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም ቦምብ ሲወረውሩ የተባበራቸው ጀግና ነው። በታክሲው ይዟቸው መጭ ያለ ልበ ደፋር ሰው ነው። በኢትዮጵያ የታሪክ አለም ውስጥ ስለ እሱ ብዙ አልተባለለትም።
ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ስለዚሁ ስምኦን አደፍርስ ስለሚባለው አስገራሚ ኢትዮጵያዊ ሰፋ አድርገው ከጻፉ ሰዎች መካከል አንዱ ናቸው።

ስምኦን ከአባቱ ከአቶ አደፍርስ አድጎ አይቸውና ከእናቱ ከወይዘሮ ሙሉ ብርሃን መሸሻ በሐረርጌ ክፍለ ሀገር በሐብሮ አውራጃ በአንጫር ወረዳ ልዩ ስሙ ጉባ ላፈቶ በሚባለው ሥፍራ በ 1905 ዓ.ም ተወለደ። እድሜው ለትምህርት ሲደርስ በመጀመሪያ እዚያው ላፍቶ በሚገኘው የካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ደብር ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በሕፃንነቱ በመምጣት በልደታ ማርያም ካቴድራልና በአሊያንስ ፍራንሴዝ ትምህርቱን በሚገባ አጠናቀቀ። ከዚያም በታክሲ ነጂነት ወደ ግል ሥራ ተሠማርቶ ይኖር ነበር።.......

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/1JKUmZzf5p/

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Feb, 16:47


የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 81 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን በአብርሃም ደቦጭ እና ሞገስ አስገዶም መሪነት በኢጣልያኑ የጦር አዛዥ ጄነራል ግራዚያኒ ላይ በቦንብ ያደረጉት የግድያ ሙከራ ምክንያት የኢጣሊያን ወታደሮች በቂም በቀል በመነሳት በሺዎች የሚቆጠሩ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችን ለ 3 ተከታታይ ቀናት ዘግናኝ እና ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ በህዝቡ ላይ ጭፍጨፋ ያደረሱበት ዕለት ነበር።

የካቲት 12 ቀን 1929 ዓ.ም በፋሺስት ኢጣሊያ በግፍ የተጨፈጨፉ ኢትዮጵያውያን ሰማዕታት ሲታወሱ......

የካቲት 12 ቀን በኢትዮጵያ ታሪክ የተለየ ቀን ነው፡፡ የኢጣሊያዋ ኔፕልስ ግዛት ልዑል ልጅ መውለዱን ለመዘከር ግራዚያኒ በዚህ ቀን የአዲስ አበባን ደሃዎች ሰብስቦ ለመመጽወት ባደረገው ጥሪ መሰረት ከ 3ሺ የሚበልጡ አቅመ ደካሞች በጥዋቱ በ 6 ኪሎው ቤተመንግስት ተገኝተዋል፡፡

በዚህ ቀን ኢትዮጵያውያን ጥቃት ሊያደርሱ ይችላሉ የሚለው መረጃ እስከ ሮም በመሰማቱ የቤተመንግስቱ ውስጥና ዙሪያ መትረየስ በታጠቁ ልዩ ወታደሮች እንዲጠበቅ ተደርጓል፡፡ አብርሃ ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ይህንን ጠንካራ ጥበቃ አልፈው ውስጥ ገብተዋል፡፡

ከቀኑ ለስድስት ሩብ ጉዳይ አካባቢ ሲሆን ከፍተኛ ፍንዳታ በቤተ መንግስቱ ተሰማ፡፡ ከፍ ወዳለው የቤተመንግስቱ ደረጃ የተወረወረው ቦምብ ደግሞ ግቢውን በጩሀት አናጋው፡፡ የመጀመሪያው ቦምብ ባለመትረየስ ጠባቂውን አስወገደው፡፡ 2ኛው ቦምብ ከግራዚያኒ አጠገብ የነበረውን ምሰሶ አፈራረሰው፡፡......

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/18eTRqoJUT/

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Feb, 19:35


የእንግሊዟ ንግስት ኤልሳቤት ፪ኛ ለጉብኝት ወደ ሀገራችን ከመምጣታቸው ከቀናቶች በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ላይ የተደረገው ዝግጅት ፤

ታህሳስ -- 1957 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Feb, 17:16


የካቲት 11 ቀን 1909 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 108 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ለራስ ወ/ጊዮርጊስ አቦዬ ዘውድ ጭነውላቸው የጎንደር ሰሜን ንጉስ አድርገው የሾሟቸው ዕለት ነበር።

ራስ ወ/ጊዮርጊስ አቦዬ ጧት በማለዳ ወደ መንበረ መንግሥት ቅ/ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሄደው ቅዳሴ አስቀደሱና ወደ ግቢ ገቡ ፣ ከጧቱ 2:00 ሰዓት ሲሆን አቡነ ማቴዎስና እጨጌ ወ/ጊዮርጊስ ፣ ራሶችና ሚኒስትሮች ደጃዝማቾችም ወደ ግቢ መጥተው በትልቁ ዳስ ውስጥ በየማዕርጋቸው ተቀምጠው ይጠባበቁ ጀመር፡፡ ከዚህ በኋላ ንግሥት ዘውዲቱ ከልዑል አልጋወራሽ ተፈሪ ጋር ወደ ትልቁ ዳስ ወረዱ።

በዚህ ጊዜ የገንዘብ ሚኒስትሩ ዘውዱንና ቀጸላውን ከንግሥቲቱ ፊት አቀረቡ። እጨጌ ወ/ጊዮርጊስም ዘውዱን አንሥተው ይዘው ወደ ጳጳሱ ወስዱና ጳጳሱ ዘውዱን ባርከው ለንግሥቲቱ አቀረቡ ፣ ግርማዊት ዘውዲቱም ቀጸላውን ለራስ ወ/ጊዮርጊስ በራሳቸው ላይ አሠሩላቸውና ዘውዱን ደፉላቸው ቀጥሎም እንዲህ አሉ ፤ " ሃይማኖታችንንና መንግሥታችንን ፣ አገራችንንና ሕዝባችንን እንድትረዳበት ይህን ዘውድ ሰጥቼሃለሁ ፣ እግዚአብሔር የእውነትና ያንድነት የመስማማትና የጤና ዘውድ ያድርገው" ብለው የምርቃት ቃል ተናገሩ።

ወዲያው በንግሥቲቱ ቀኝ አልጋ ተዘረጋና ንጉሥ ወ/ጊዮርጊስ ዘውድ እንዳደረጉ በአልጋው ላይ ተቀመጡ፡፡ አንድ ሊቀ መኳስም ተፈቀደላቸው በዚህ ጊዜ ሕዝቡ ስለ ደስታ አጨበጨበ፣ መሳፍንቱና መኳንንቱም እጅ እየነሡ ቆሙ።

ከዚህ በኋላ ንጉሥ ወ/ጊዮርጊስ ከንግሥት ዘውዲቱ ተሰናብተው ወደ ቤታቸው ለመሄድ ሲነሡ በወርቅ መረሻትና በወርቅ ዕቃ ያጌጠች በቅሎ ቀረበላቸውና እዚያው እዳሱ ውስጥ በበቅሎ ተቀምጠው በፊት ሰጥቼሃለሁ።.....

ሙሉውን ታሪክ
👇
https://vm.tiktok.com/ZMk7fmvXR/

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

16 Feb, 16:24


የመጣው ይምጣ ከሞት ውጪ የሚመጣ የለም። ነገሩ ከአቅም በላይ ከሆነ ሻዕቢያ ዓይኔን ማየት ቀርቶ ሬሣዬንም አያገኛትም። እድሜ ለቀይ ባህር ውሃ የቀይ ባህር ዓሳ ይቀብረኛል።

የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግስት ጣሉብኝ አደራ ከድንጋይ በላይ ይከብደኛል በመሆኑም ጠላት ከአቅም በላይ ከሆነ እንደ አጼ ቴዎድሮስ ሽጉጤን እጠጣለሁ፡፡

የካቲት 9 ቀን 1982 ዓም ምጽዋ ከተማ ለተከማቸው አብዮታዊ ሠራዊትና አመራሩ ክፉ ቀን ነበረች ሻዕቢያ ደግሞ እንደ ልደት ቀን ይቆጠረዋል ምክንያቱም የሻዕቢያ ተዋጊ የድል ባለቤት ሆኖ ለመጀመሪያ ጊዜ ምፅዋ ከተማን የረገጠው በዚች ዕለት ነውና ሻዕቢያ በ 1970 ዓ.ም ከጀብሃ ተዋጊዎች ጋር በመሆን አብዛኛውን የኤርትራ ግዛት ተቆጣጥሮ ነበር፡፡

አሥመራ ባሬንቱ ምፅዋና ዓዲ ቀይህ ከተማ የነበሩትን የአብዮታዊ ሠራዊት አባላት ደምስሶ እነዚህን ከተሞች መቆጣጠር አልቻለም፡፡ በመሆኑም የሃያ ስምንት ዓመታት ምኞቱን ሻዕቢያ በምፅዋ እውን ያደረገበት ቀን የካቲት 9 ቀን 1982 ናት፡፡

ጄኔራል ተሾመ ተሰማ የካቲት 9 ቀን 1982 ዓ.ም ከጠዋቱ 1፡30 ሰዓት ላይ በምፅዋ ከተማ ርዕሰ ምድርዕ በተባለ አካባቢ በከባድ መሳሪያ በፈራረሱ ቤቶች ጥግ ሆነው የተወሰኑ የጦር መኮንኖችንና ባለሌላ ማዕረግተኞችን ሰብስበው ንግግር አደረጉ፡፡

ሻዕቢያ ያለ የሌለ ሃይሉን ተጠቅሞ በእጅ ቦምብና በክላሽ በአሁኑ ሰዓት የከተማ ውስጥ ውጊያ በማድረግ ላይ ነው፡፡ ሻዕቢያ የከባድ መሳሪያ ድብደባ አቁሞ በእግረኛ ብቻ ለመዋጋት አዲስ ተዋጊ ሃይሉን በመኪና እያመላለሰ ዕዳጋ ከተማ ላይ እያከማቸ ነው፡፡ በአዲስ ጉልበት ተዋግቶ ምፅዋን ለመያዝ ቆርጦ ስለመነሳቱ ጥርጥር የለውም፡፡.....

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/14GXxpR6aS/

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

16 Feb, 13:14


የኢትዮጵያ ብሔራዊ ኤክስፖ ዝግጅት በአስመራ ከተማ በተዘጋጀበት ወቅት ፤ 1964 ዓ.ም

The Ethiopian National Expo in Asmara Back in 1972

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Feb, 15:22


የቅዳሜ ገበያ በአራዳ ፤ አዲስ አበባ

1920 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Feb, 11:48


ሠናይ ቅዳሜ ይሁንላችሁ 🙏

"የኢትዮ-ጃዝ ሙዚቃ አባት"
አርቲስት ሙላቱ አስታጥቄ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Feb, 10:19


የግርማዊት እቴጌ መነን አስፋው የቀብር ሥነስርዓት ሲፈፀም ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Feb, 09:22


የካቲት 8 ቀን 1954 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 63 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ባለቤት ግርማዊት እቴጌ መነን አስፋው ያረፉበት ዕለት ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Feb, 20:49


የዩጎዝላቪያ ፕሬዝዳንት ማርሻል ቲቶ በኢትዮጵያ ይፋዊ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት ፤

ታህሳስ -- 1948 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Feb, 18:53


አዲስ አበባ ከተማ በዘመኗ ፤

በ 1960 ዎቹ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Feb, 18:41


ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከልጃቸው ከልዕልት ፀሐይ ጋር በሊንከን ሐውስ ፣ ፓርክሳይድ ውስጥ ሆነው ሻይ እየጠጡ ፤

ሰኔ -- 1928 ዓ.ም
ለንደን

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Feb, 17:46


ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴና የብሪታኒያ ንግስት ኤልዛቤት ልጅ ከሆነችው ልዕልት አን ጋር በምፅዋ የኢትዮጵያ የባህር ኃይል የካዴቶች የምረቃ ሥነ-ሥርዓት በተካሄደበት ወቅት ፤

ጥቅምት -- 1966 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Feb, 17:20


በ 1948 ዓ.ም በኢትዮጵያ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ሕንዳውያን አስተባብረው ያስቀረፁት እና በአዲስ አበባ ሲኒማ አምፒር አጠገብ ቆሞ የነበረ የቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ሐውልት ነበር።

ሆኖም ይህ ሐውልት ከዓመታት በኋላ ማለትም በወርሃ መስከረም 1967 ዓ.ም ወታደራዊ የደርግ መንግስት ወደ ስልጣን በመጣበት ወቅት ሐውልቱን አፍርሶታል።

ሐውልቱ ላይ የተፃፈው ጽሑፍ :-

"በኢትዮጵያ የምንኖር የሕንድ ተወላጆች ሁሉ በሥራችን እና በኑሮአችን ደስ ስላለን ለግርማዊ ንጉሠ ነገሥት ቀጻማዊ ኃይለሥላሴ 25ኛው የዘውድ በዓል ኢዮቤልዩ ይህንን ሐውልት መታሰቢያ አቅርበናል"።

ጥቅምት 23 ቀን 1948 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Feb, 19:02


የካቲት 6 ቀን 1988 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 29 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ሜ/ጀ ሓየሎም ኣርኣያ (ሓዱሽ) የተገደለበት ዕለት ነበር።

ገዳዩ ጀሚል ያሲን በእስር ቤት ሳለ ከእፎይታ መፅሄት አዘጋጅ ጋር ያደረገው ቃለመጠይቅ ፤

"የሞት ቅጣት ተፈርዶብሃል ይሄ ፍትሃዊ ነው "?

<<ለእኔ ሞት ያንሳል! ጀነራል ሀየሎምን ያጠፋ ሰው ከሞት በላይ ይገባዋል>>
.
.
ጋዜጠኛ:- ችግሩ ከመፈፀሙ በፊት ከሀየሎም ትተዋወቁ ነበር?

ጀሚል:- ከመጄር ጀነራል ሀየሎም አ ጋር አንተዋወቅም፡፡ መተዋወቅ ግን እፈልግ ነበር፡፡

ጋዜጠኛ:- ለምን?........

ሙሉውን ታሪክ
👇
https://vm.tiktok.com/ZMktxMVp3/

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

10 Feb, 19:37


#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Feb, 20:14


አንጋፋዎቹ የሀገራችን የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች ህልፈተ ህይወታቸው በወርሃ የካቲት ላይ....

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Feb, 18:23


ግርማዊ ጃንሆይ የቀድሞው መጠሪያ ስሙ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የአሁኑ የካቲት 12 ሆስፒታል ውስጥ ታካሚዎችን እየተዘዋወሩ ሲጠይቁ ፤

1947 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Feb, 16:59


ሌ/ኮሎኔል አጥናፉ አባተ ፤

የኀብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ
፪ኛ ምክትል ሊቀመንበር ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Feb, 16:27


የካቲት 1 ቀን 1972 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 45 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን አንጋፋው ደራሲና ጋዜጠኛ አቤ ጉበኛ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየበት ዕለት ነበር።

ዕለቱ ቅዳሜ ምሽት ነው፡፡ ወሩ የካቲት 1 ቀን 1972 ዓ.ም ቦታው ደግሞ አዲስ አበባ ጐጃም በረንዳ አካባቢ፡፡ ታላቁ ኢትዮጵያዊ የጥበብ ሰው አቤ ጉበኛ ቀበሌ 34 አካባቢ ከአስፋልቱ ዳር ተዘርግቶ ወድቋል፡፡

ጐጃም በረንዳ አካባቢ የሚኖሩ አቤን የሚያውቁ ሰዎች ተጠርተው መጡ፡፡ አቤ ‘‘አንሱኝ፣ አንሱኝ፣ ተጠቃሁ…’’ እያለ ያቃስታል፡፡ የመጡት ሴቶች ናቸው፡፡ ሊያነሱት ሞከሩ፡፡ ጐተቱት፡፡ ሊሳካላቸው አልቻለም፡፡ ሌሎችም ተሰበሰቡ፡፡ ኃይል ሲገኝ አነሱት፡፡ ከዚያም የወሰዱት ሆስፒታል አልነበረም፡፡ አቤ ቀደም ብሎ ‘‘አርባ ምንጭ’’ የሚባል ሆቴል ውስጥ መኝታ ክፍል ተከራይቷል፡፡ እናም ወደ መኝታ ክፍሉ ወስደው አስተኙት፡፡

ሲነጋ ማለትም እሁድ ጠዋት ፖሊሶች መጥተው ወደ ጳውሎስ ሆስፒታል ወሰዱት፡፡ ሆስፒታል ከገባ ከግማሽ ሰዓት በኋላ ዶክተሮቹ አቤ ጉበኛ መሞቱን አረጋገጡ፡፡ ‘ተጠቃሁ’ እያለ ሲያቃስት የነበረው አቤ ጉበኛ ማን መታው? ምን ሆኖ ሞተ?

ሞቱ ከተነገረ በኋላ ቀብሩ ታሰበ፡፡ ማን ይቅበረው? ከ20 መፃህፍት በላይ ያሳተመ ጐምቱ ደራሲ ቀባሪ አጣ፡፡ ማን ደፍሮ ሬሳውን ወስዶ ይቅበረው? ማዘጋጃ ቤት ሊቀብረው ዝግጅት ላይ እያለ ሲራክ ቀለመወርቅ የተባሉ ሰው ‘አቤን ቀበርሁና አልቀበርኩኝ ምን እንዳልኮን ነው ብዬ ቆርጬ ገባሁበት’ ብለው ገቡበት፡፡ በኋላም አስከሬኑ መመርመር አለበት ብለው በፖሊስ ወደ ዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል ተወሰደ፡፡ ተመረመረ፡፡ ውጤቱ ምን ይሆን? አቤን ምን ገደለው?

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/1BE9gUEi2h/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Feb, 20:21


ሌ/ኮ ዳንኤል አስፋው ሰባቱን ሰዎች ከረሸናቸው ከሰዓታት በኋላ ከሻለቃ ዮሐንስ በተተኮሰበት ጥይት ህይወቱ ሲያልፍ በወቅቱ በቤተመንግስት ውስጥ የነበረው ክስተት የሚያሳይ ብርቅዬ ቪዲዮ ፤

ጥር 26 ቀን 1969 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Feb, 18:55


መዲናይቱ አዲስ አበባ ከተማ በዘመኗ ፤

በ 1950ዎቹ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Feb, 17:51


4 ኪሎ የሚገኘው (የአርበኞች የድል ሐውልት) ቦታ ላይ በፊት ቆሞ የነበረው በአክሱም አምሳያ የተሰራው ሐውልት ታሪክ ፤

በጥንታዊቷና ታሪካዊቷ በአክሱም ከተማ እንደ ቀድሞዎቹ ነገስታት ቤተክርስቲያን ለማሰራትና የስም መታሰቢያ ለማኖር የግርማዊ ጃንሆይ ምኞት ስለነበር ይህንን ሀሣባቸውን ለመተግበር የሥራ ሚኒስቴሩ ፊታውራሪ ታፈሰ ሀብተሚካኤል የቦታውን ፕላን አስጠንተውና አዘጋጅተው እንዲያቀርቡ ታዘው ከመሐንዲሶች ጋር በባቡር ተሳፍረው በጅቡቲ በኩል ወደ ምጽዋ ተጓዙ፡፡

ከዚያም በአስመራ ላይ አልፈው አክሱም ገብተው የቦታውን ፕላን ሲያስጠኑ ሰነበቱ፡፡ ወጣቱ ልጅ ተድላ ኃይሉም ራፖርት ለማድረግ አብሮ ሔደው ነበር፡፡ ፊታውራሪ ታፈሰ በአክሱም የቦታውን ፕላን አስጠንተውና የሐውልቶቹን ሥዕል በፎቶግራፍ አስነስተው ካበቁ በኋላ በሄዱበት መንገድ ወደ አዲስ አበባ ተመለሱ፡፡

ግርማዊ ንጉሰ ነገሥትም ፕላኑን ስለአሰራሩ ያስቡበት ጀመር፡፡ የሐውልቱንም ሥዕል ተመልክተው በዚያ አምሳል አንድ ሐውልት አዲስ አበባ አራት ኪሎ በሚባለው ሥፍራ ላይ እንዲሰራ ለሥራ ሚኒስትሩ ትዕዛዝ ሰጡ፡፡ ፊታውራሪ ታፈሰም የሐውልቱ ግንባታ ሥራ በቶሎ አስጀምረው አስገንብተውታል።

ይህ ሐውልት ኢጣልያኖች በወራሪነት አዲስ አበባ በገቡበት ዘመን በ1928 ዓ.ም ከወደ ሥሩ በመዶሻ ሰባብረውና አፍርሰው በትሬንታ ኳትሮ ካሚዮን አስጎትተው ጥለውታል፡፡

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Feb, 16:24


ዩኒፎርም ለብሰው በጎዳናዎች ላይ ሰልፍ የወጡ ወንዶች ተማሪዎች ፤

አዲስ አበባ ፤ ጥር -- 1929 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Feb, 14:34


የቀድሞው የጦር ሠራዊት ወታደሮች ፤

አዲስ አበባ ፤ ታህሳስ -- 1952 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Feb, 13:33


ጥር 27 ቀን 1842 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 175 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ራስ ሚካኤል በፈረስ ስማቸው “አባ ሻንቆ” እየተባሉ የሚታወቁት የደሴ ከተማ መስራች፣ የወሎው ባላባት፣ የአቤቶ ልጅ እያሱ አባት፣ የእቴጌ መነን አያት ንጉስ ሚካኤል የተወለዱበት ዕለት ነበር።

ንጉሥ ሚካኤል ከአባታቸው አሊ አባ ቡላ እና ከእናታቸው ጌይቲ ገባቤ ጥር 27 ቀን 1842 ዓ.ም ተወለዱ። የቀድሞ መጠሪያቸው መሐመድ አሊ አባቡላ የነበረ ሲሆን በአጼ ዮውሃንስ ዘመነ መንግሥት በ 1870 ዓ.ም በቦሩ ሜዳ በተደረገው ሃይማኖታዊ ጉባዔ ላይ ክርስትናን ከተቀበሉ በኋላ ራስ ሚካኤል በመባል የወሎ ገዢ ሆነው ተሹመዋል፡፡

በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ዘመንም ከቤተመንግሥት ጋር የጋብቻ ትስስር መፍጠራቸው ስማቸው በይበልጥ እንዲታወቅ አስችሏቸዋል፡፡ ቀስ በቀስ ግዛታቸውን እያጠናከሩም ሄድዋል፡፡ በልጃቸው በአቤቶ ኢያሱ ዘመን ደግሞ ሰፊ ግዛት ተጨምሮላቸው በንጉሥነት ማዕረግ ከፍ ብለው የሰሜኑን የሀገሪቱን ክፍል በእርሳቸው አስተዳደር ሥር ሆነዋል።.....

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/1AvLjXF4pE/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Feb, 10:37


ከ 48 ዓመት በፊት ጥር 26 ቀን 1969 ዓ.ም የኢህአፓ ደጋፊዎች ተብለው የተፈረጀባቸው የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር የነበሩት ጀነራል ተፈሪ በንቲ እና ሌሎች 6 ግለሰቦች ላይ በደርግ ዘመቻና ጥበቃ ኃላፊ በሌ/ኮሎኔል ዳንኤል አስፋው አማካኝነት ድምፅ ማፈኚያ (Silencer) በተገጠመለት መሳሪያ ሽጉጥ የተገደሉበት ዕለት ነበር።

⩩ በወቅቱ በሰባቱ ግለሰቦች ላይ የተወሰደው እርምጃ በብሔራዊ ራዲዮ የተላለፈው እና በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ የወጣው ፅሁፍ

"....በመለዮ ለባሹ መሀከል መከፋፈል በመለዮ ለባሹና በሰፊው ሕዝብ መካ ልከ መቃቃርን እያስፋፉ በሔዱት በኢሕአፓና በኢዲዩ የውስጥ አርበኞች ላይ አብዮቱ ከመጠቃት ወደ አጥቂነት በመሸጋገር ዛሬ የማያዳግም አብዮታዊ ርምጃ ወስዶባቸዋል።

በዚህም መሠረት በጊዜያዊ ወታ ደራዊ አስተዳደር ደርግ ውስጥ ለኢ አፓና ለኢዲዩ በውስጥ አርበኝነት ብዮቱን ለመቀልበስ ተራማጅ የደርግ አባላትንና የሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት ታጋዮችን ለማፈን ሲያሴሩ እጅ ከፍንጅ በተ ያዙት በሚከተሉት የውስጥ አርበበኞች ላይ በትናንቱ ዕለት አብዮታዊ ርምጃ ተወስዶባቸዋል። እነርሱም:-......

፩. ብ/ጀነራል ተፈሪ በንቲ:- የደርግ ሊቀምንበር
፪. ሌ/ኮ አስራት ደስታ:- የማስታወቂያ ጉዳይ ም/ኃላፊ
፫. ሌ/ኮ ህሩይ ኃ/ስላሴ:- የህዝብ ደህንነትና መረጃ ዘርፍ ሃላፊ)
፬. ሻምበል ሞገስ ወ/ሚካኤል :- የውጭ ጉዳይና የህዝብ ማደራጃ ዘርፍ ሃላፊ)
፭. ሻምበል አለማየሁ ሃይሌ:- የደርጉ ዋና ፀሃፊ
፮. ፲ አለቃ ሃይሉ በላይ:- የውጭ ጉዳይና የህዝብ ማደራጃ ዘርፍ ምክትል ሃላፊ)
፯. ሻምበል ተፈራ ደነቀ:- የደርግ አባል

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/1BKk9TiHXX/

#ታሪክን_ወደኋላ

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Feb, 09:35


ጥር 27 ቀን 1957 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 60 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት ሕንፃ ግንባታ አልቆ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ተመረቆ የተከፈተበት ዕለት ነበር።

ጥቅምት 23 ቀን 1942 ዓ.ም በግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አራዳ የሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ሕንፃ ግንባታ ለማስጀመሪያ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጡ ቀን ሲሆን ፣ የህንፃው ያስገነባው ጣልያናዊው አርክቴክት አርትሮ ሜዜዲሚ ይባላል። ይህ ህንፃ 600 መቶ ልዮ ልዮ ክፍሎች ያሉትና የመኪና ማቆሚያና መናፈሻ ቦታ ጨምሮ 75 ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈው ሲሆን ተመርቆ የተከፈተው ግንባታው ከተጀመረ ከ 15 ዓመት በኃላ ጥር 27 1957 ዓ.ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ ነበር።

በሕንፃው መግቢያ ላይ የተለጠፈው ሰሌዳ እንዲህ ይላል፤

«ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ለመናገሻው ከተማ ለአዲስ አበባ ሕዝባቸው፣ ለማኅበራዊ ኑሮው፣ ለኤኮኖሜውና ለባህሉ ዕድገት አማካይ የአገልግሎት ቤት ይሆን ዘንድ ፈቅደው ያሠሩትን ይህን ሕንፃ፣ በሠላሳ አራተኛው ዘመነ መንግሥታቸው መርቀው ከፈቱ።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

03 Feb, 17:39


ደራሲና ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የክብር የ ፲ አለቅነት ማዕረግ ያገኙት ጋዜጠኛ ጳውሎስ ኞኞ በ ፲፱፻፶፯ ዓ.ም ኢትዮጵያና ሶማሊያ ጦርነት ወቅት በኦጋዴን ጠረፍ ግዳጃቸውን ሲያከናወኑ የተነሱት ፎቶግራፍ ነው።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

03 Feb, 17:26


የኢትዮጵያ ቱሪዝም ኮምሽን 1970ዎቹ "የ 13 ወር ፀጋ (ETHIOPIA 13 Months Of Sunshine) በሚል ርዕስ ካሳተማቸው ፖስተሮች መካከል በመሀል ድሬዳዋ ከተማ የሚገኘውን "በከዚራው ጥላው ስር" የተባለለት ከዚራ ሰፈር ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

03 Feb, 17:15


አቶ በላይ ተክሉ ፤

የበላይ ተክሉ ኬክ ቤት ባለቤት

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

03 Feb, 12:29


የቀድሞ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪዎች ጋር በዩኒቨርስቲው ዋናው (ስድስት ኪሎ) ግቢ ፣ በኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ኢንስቲትዩት ፊት ለፊት የተነሱት ፎቶግራፍ ፤

1973 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Feb, 17:39


የኢትዮጵያ እና የጋና ብሔራዊ ቡድን የወዳጅነት ጨዋታ ፤

ኢትዮጵያ 2 -- 0 ጋና

አዲስ አበባ ፤ ጥር - 1968 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Feb, 16:13


የንግድ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የምርቃት ስነ-ስረዓት ፤

በምስሉ ላይ እንደሚታየው የምርቃት ስነ-ስረዓቱ ላይ ልዑል አልጋወራሽ ራስ ተፈሪ መኮንን ፣ መኳንንቶች እንዲሁም በተጋባዥነት የቤልጂየም ፣ ጣሊያን ፣ ፈረንሳይ እና የአሜሪካ ሀገራት የሚኒስትር ኃላፊዎች በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተዋል።

ጥቅምት -- 1921 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Feb, 15:21


"ሠናይ ዕለተ ቅዳሜ ይሁንላችሁ" 🙏

ጥንታዊቷና ታሪካዊቷ አኽሱም ከተማ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

28 Jan, 18:43


የአፄ ፋሲለደስ ቤተ-መንግስት

ጎንደር ፤ በ 1940ዎቹ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

28 Jan, 18:31


የፖሊስ ሠራዊቱ ፊልም ለማየት በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቲያትር ቤት ፊት ለፊት ተሰልፈው ይታያሉ ፤

ጥቅምት -- 1950 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

28 Jan, 16:50


ጥር 20 ቀን 1913 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 104 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ሀገር ወዳዱ ፣ ጀግናው አርበኛ ሌ/ጄነራል ጃጋማ ኬሎ ‹‹የበጋው መብረቅ›› የተወለዱበት ዕለት ነበር።

www.facebook.com/share/p/14kux6Wz9Y/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

27 Jan, 19:30


ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በሀገረ ጃማይካ ኪንግስተን ከተማ ላይ በተደረገላቸው የእንኳን ደህና መጡ የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት ላይ የራስ ተፈሪያን ልዑካን መሪዎች ለንጉሡ ሰላምታ ሲያቀርቡ ፤

ሚያዝያ -- 1958 ዓ.ም
ጃማይካ-- ኪንግስተን

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

27 Jan, 19:06


ልጅ ሳልሳዊ ሚኒሊክ እያሱ

ልጅ ሚኒሊክ ሳልሳዊ የአቤቶ ልጅ እያሱ ልጅ ሲሆኑ የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ደግሞ የልጅ ልጅ ልጅ ናቸው፡፡ የልጅ ሚካኤል ሳልሳዊ ወላጅ እናት የአፋሯ ፋጡማ መሐመድ አቡበከር ባሻ ይባላሉ፡፡

የፋጡማ ወላጅ አባት የታጁራ ሱልጣኔት "የነጋድራስ መሀመድ" ልጅ ሲሆኑ ይኸውም በዘር ሀረጋቸው በዘይላ ሀሶባ ውስጥ ካለው የአፋር ኦባካርቶ የሚመዘዝ ያደርገዋል።

አቤቶ ልጅ ኤያሱ እና ፋጡማ መሐመድ የተጋቡት በ 1909 ዓ.ም ላይ ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

27 Jan, 15:26


የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የልጅ ልጆች በምጽዋ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ባህር ኃይል ሲጎበኙ ፤

ጥር -- 1952 ዓ.ም
ምጽዋ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

27 Jan, 11:54


በሮም ኦሎምፒክ የተሳተፈው ኢትዮጵያ የብስክሌት ተወዳዳሪ ቡድኖች ፤

ጳጉሜ -- 1952 ዓ.ም
ሮም -- ጣሊያን

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

27 Jan, 11:39


እጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) ዋና መሥሪያ ቤት አዳራሽ ውስጥ የሚገኘው የስዕል ስራቸውን ለልዕልት አን ገለፃ ሲያደርጉ ይታያሉ ፤

ልዕልት አን የታላቋ ብሪታንያ ንግሥት ኤልዛቤት ፪ኛ እና የልዑል ፊሊፕ ብቸኛ ሴት ልጅ ናቸው።

የካቲት -- 1965 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

27 Jan, 07:47


ሚያዝያ 27 ቀን ሆቴል ፤ Bar & Restaurant

ጎንደር -- 1965 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

26 Jan, 16:52


የድል ሐውልት (አራት ኪሎ) በዘመኑ ፤

አዲስ አበባ -- በ 1950ዎቹ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

26 Jan, 15:29


ጥር 18 ቀን 1879 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 138 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬው ቀን ራስ አሉላ እንግዳ (አባ ነጋ) ወዲ ቁቢ በኤርትራ በምትገኘው ዶጋሊ ላይ ድንበር ጥሶ ለመውረር የሞከረውን ጣሊያን ጦር ጋር ገጥመው አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ድል የተቀናጁበት ዕለት ነበር።

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/1BbA9S8y6H/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

26 Jan, 14:34


ጥር 18 ቀን 1957 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 60 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የታላቋ ብሪታኒያ ዳግማዊት ንግሥት ኤልሣቤጥ የፊልድ ማርሻል (Field Marshal) ማዕረግ ለግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የሰጡበት ዕለት ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

26 Jan, 14:09


የድሬዳዋ ቤተመንግሥት ፤ "የሠላም አዳራሽ"

Dire Dawa Palace "Peace Hall"

በ 1930 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

24 Jan, 21:11


የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ኃይለሥላሴና የልጅ ልጃቸው ልዕልት እጅግአየሁ አስፋወሰን ለሁለት ቀናት ጉብኝት ወደ ሀገረ ጣሊያን በሄዱበት ወቅት ፕሬዚዳንት ጁሴፔ ሳራጋት የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ሲያደርጉላቸው ፤

ህዳር -- 1963 ዓ.ም
ኢጣሊያ -- ሮም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

24 Jan, 19:50


ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ

ከመስከረም 17 ቀን 1909 ዓ.ም እስከ መጋቢት 24 ቀን 1922 ዓ.ም ድረስ ፤ ለ 13 ዓመት ከ 6 ወር ያህል ዓመታት በንግስተ ነገሥታት ዙፋን ላይ ተቀምጠው ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ በኢትዮጵያ ዘመናዊ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት የሀገር መሪ ናቸው፡፡

⨳ ሙሉውን የህይወት ታሪካቸው
👇
www.facebook.com/share/p/1DWocR9Qkr/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

24 Jan, 19:29


የጥጥ ነጋዴ በዘመኑ ፤

ባቲ -- 1930 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

24 Jan, 18:18


ከ 99 ዓመት በፊት ታትሞ የወጣው "አዕምሮ ጋዜጣ"

ስለ : ታላቋ : ተራራ : የብልሆች : እርስት።

በውኑ ጥበብ አትጮኸምን ልባዊ ድምፅዋን አትስጥምን። በተራራ ኮረፍታ ላይ በመንገድ አጠገብ በጐዳና መካከል ቆመች በከተማው ደጅ ጥግና ባደባባዩም ደጅ መግቢያ ትጮኸለች።

ክቡራን የኢትዮጵያ ልጆች ባለፈው ሳምንት "አእምሮ" ስለ አእምሮ የእውቀት ተራራ ብርቱዎች እንዲደርሱባት ደካሞች ግን እንዳይችሉ በመልካም ምሳሌ የገለጸላችሁን ትከተሉ ዘንድ ደስ ይለናል።

እንዲሁም እያንዳንዳችሁ በዚች ታላቅ ተራራ የከፍታዋን ብዛት የመንገዱዋን እርዝመት ሳትመለከቱ በጽኑ ልብ በብርቱነትና በኃይለኝነት እንድነት ገጥማችሁ በረጅሙ መንገድ ጉዞዋችሁን ጀምራችኋልና ግፉ።

ነገር ግን በሰውነታችሁ ስንፍናንና መታከትን ፤ አግብታችሁ ከዚች ተራራ ቁልቁል ለመውረድ ብታስቡ በተራራዋ ጫፍ ላይ ያሉ የእውቀት ርስት ባላንወች እንዳይስቁባችሁ። ለጐረቤቶቻቸውም እንደዚህ እንዳይሉ እዩ እነዚህን ስነፎች እያዘገሙ በየጥላው እያረፉ በዝግታ ይህችን ተራራ 1 መውጣት አቅቶዋቸው ልባቸውን ወደታች አድርገውታልና የታችኛውን የአባታቸውንውን እርስትና ጉልበት መመኪያ አድርገው ተመለሱ።

ጉልማሶች ወንድሞቻችን ሆይ እንደዚሁም ይህችን ታላቅ በሕይወትም በሥጋም የምትጠቅም እርስታችንን ለመውረስና ለመያዝ እንጣጣር እንጅ ልባችን ወደታች አድርገን መንገዱዋን ታስብነውስ ከደረጃ በታች መኖር ነው።....

ሙሉውን ፅሁፍ
👇

www.facebook.com/share/p/18Q4VdR42T/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

24 Jan, 15:40


ልዑል መኮንን ኃይለሥላሴ እና ባለቤታቸው ልዕልት ሳራ ግዛው በጌልድሮፕ ከተማ ውስጥ የሚገኘውን "DAF" የመኪና ፋብሪካ ጉብኝት ሲያደርጉ ፤

ጥቅምት -- 1954 ዓ.ም
ኔዘርላንድ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

20 Jan, 19:55


የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት (ፓርላማ)

አዲስ አበባ ፤ ጥር -- 1952 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

20 Jan, 17:58


ጥር 12 ቀን 1933 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከዛሬ 84 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ግርማዊ ለቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከሱዳን ወደ ኢትዮጵያ መሬት ገብተው ኦሜድላ (በጎጃም ክፍለ ሃገር) ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ የሰቀሉበት ዕለት ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

20 Jan, 12:08


የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ኦታዋ ማክዶናልድ - ካርቲየር ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ የልጅ ልጃቸው ልዑል ሚካኤል መኮንን እና የልጅ ልጅ ልጃቸው ልዑል ሚካኤል መንገሻ የእንኳን ደህና መጡ አቀባበል ሲያደርጉላቸው።

በወቅቱ ልዑል ሚካኤል መኮንን እና ልዑል ሚካኤል መንገሻ በኦታዋ በሚገኝ የግል ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ነበር።

ካናዳ - ኦታዋ
መስከረም -- 1956 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Jan, 20:40


የኢዮ-ቤልዩ ቤተመንግሥት ፤ አዲስ አበባ

ታህሳስ 1962 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Jan, 16:29


ከ 107 ዓመት በፊት የጥምቀት በዓል አከባበር ፤

በ 1910 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Jan, 16:10


የክብር ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ

የቀድሞ ባለቤቱ ሆስተስ ፌሪያል አህመድ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Jan, 15:37


አቤቶ ልጅ እያሱ ሚካኤል እና

ደጃዝማች ተፈሪ መኮንን በኋላ (ቀ.ኃ.ሥ)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Jan, 11:41


እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሠላም አደረሳችሁ 🙏

የጥምቀት በዓል አከባበር ፤

አዲስ አበባ -- በ 1951 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Jan, 20:15


ጥር 10 ቀን 1891 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 126 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት በጉንደት ፣ በገራዕ ፣ በኩፊት ፣ በዶጋሊ ፣ በዓድዋ… ከወራሪዎች ጋር ተፋልመው አንፀባራቂ ድሎችን ያስመዘገቡት የምንጊዜም የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ራስ አሉላ እንግዳ (አባ ነጋ) ህይወታቸው ያለፈበት ዕለት ነበር።

www.facebook.com/share/p/1EuoUqVZvM/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Jan, 18:14


ልዕልት ማኅፀንተ ሀብተማርያም

ልዕልት ማኅፀንተ ከአባታቸው ከደጃዝማች ሀብተማርያም ገ/እግዚአብሔር እና ከእናታቸው ከወይዘሮ የሺመቤት ጉማ የካቲት 2 ቀን 1929 ዓ.ም በነቀምት ተወለዱ።

ልዕልት ማኅፀንተ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ እና ግማዊት እቴጌ መነን የንግስና ዘውድ ከደፉ በኋላ የወለዱት የመጨረሻው ልጅ የሆነው የልዑል ሳህለሥላሴ ባለቤት ናቸው።

የኢትዮጵያ የዘውድ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት እንዲሁም የጋሞ ጎፋ ጠቅላይ አገረ ገዥ የነበሩት ልዑል ሳህለሥላሴ ከባለቤታቸው ከልዕልት ማኅፀንተ ሀብተማርያም ጋር ጋብቻቸውን የፈፀሙት እሁድ ሰኔ 7 ቀን 1951 ዓ.ም ሲሆን ፤ በትዳር ዘመናቸው ብቸኛ ልጃቸው ልዑል ኤርሚያስ ወልደዋል። ልዑል ኤርሚያስ በአሁን ወቅት በአሜሪካ የዘውድ ምክር ቤት (Crown Council) ፕሬዝደንት ናቸው።

ልዕልት ማኅፀንተ ሀብተማርያም ጡረታ ከመውጣታቸው በፊት ከተባበሩት መንግስታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት (ዩኒሴፍ) ጋር ለብዙ ዓመታት ሰርተዋል ፣ ልዕልቷ በአሁኑ ወቅት የ 88 ዓመት ዕድሜ ባለፅጋ ሲሆኑ በሀገረ አሜሪካ ዋሽግተን ዲስ የሚኖሩ ብቸኛ እና የመጨረሻዋ የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ምራት ናቸው።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Jan, 11:50


የጥምቀት በዓል አከባበር በአዲስ አበባ ከተማ

በ 1993 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

17 Jan, 19:27


የጥምቀት በዓል አከባበር በአዲስ አበባ

ጃንሜዳ -- 1961 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Jan, 19:51


#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Jan, 16:24


ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከቤተሰቦቻቸው ጋር፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

11 Jan, 17:24


በልዕልት ፀሐይ ኃይለሥላሴ መታስቢያ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ የቆመው የልዕልትነታቸው ምስል ሐውልት ፤

👇
https://youtu.be/-2y4S6Ezh6k

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Jan, 18:26


ሻቃ በልሁ (አባ ቆሮ)

እርዝመቱ 2 ሜትር ከ 20 ሳ.ሜ ፣ የክቡር ዘበኛ የማርሽ ሙዚቃ የባንዱ መሪ እና የቤኒሻንጉል ጉምዝ ተወላጁ ቁመተ መለሎው ሻቃ በልሁ (አባ ቆሮ)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Jan, 12:03


ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም

የዐፄ ዮውሃንስ ፬ኛ ቤተመንግሥት ፤ መቐለ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

07 Jan, 18:47


ኦቦ ቡልቻ ደመቅሳ ሰንበቶ እና ባለቤታቸው

ወይዘሮ ሄለን ገብረእግዚአብሔር ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

07 Jan, 15:44


አንጋፋው የምጣኔ ሀብት ባለሙያውና የፖለቲካ ሠው ፤

ኦቦ ቡልቻ ደመቅሳ ሰንበቶ ፤ ነፍስ ሄር 🙏


(1923 -- 2017)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

07 Jan, 11:51


እንኳን ለገና በዓል በሠላም አደረሳችሁ ! አደረሰን !

ለመላዉ የክርስትና እምነት ተከታዮች ፣ እንኳን የገና በዓል በሠላም አደረሳችሁ ! አደረሰን! እያልን ገፃችን መልካም ምኞቱን ይገልፃል።

ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ
የገና በዓልን ሲያከብሩ
በ 1956 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Jan, 19:38


የቀድሞዋ ቀዳማዊት እመቤት ክብርት ወ/ሮ አዜብ መስፍን ከታዋቂው የሬጌ ሙዚቃ አቀንቃኝ ቦብ ማርሌ ባለቤት ከሆነችው ከሪታ ማርሌ ጋር ፤

በአፍሪካ ዩኒት የቦብ ማርሌ የ 60ኛ ዓመት የልደት በዓሉ በተከበረበት ወቅት ፤

አዲስ አበባ ፤ የካቲት - 2005 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Jan, 19:19


የሰሜን ኢትዮጵያ ታሪካዊ ስፍራዎች - በ 1966 ዓ.ም

በቪዲዮ ላይ የጣና ሀይቅ ጥንታዊ ገዳማት ፣ ክብራን ገብርዔል ፣ መድኃኔዓለም ፣ ኪዳነ ምህረት ፣ ጎንደር ፣ ደብረብርሃን ሥላሴ ፣ ናርጋ ሥላሴ ፣ ሱሱኒዮስ ደሴት ፣ የንግሥት ምንትዋብ ቤተመንግስት በቁስቋም ፣ ላሊበላ ፣ ቤተጊዮርጊስ ፣ ቤተማርያም ፣ ቤተጎሎጎታ ሚካዔል ፣ ዱንጉር ፣ አክሱም ፣ የአጼ ካሌብ መካነ መቃብር ፣ የአክሱም ገበያ ይታያል።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Jan, 18:49


ክቡር ብላታ ደሬሳ አመንቴ ፤

ብላታ ደሬሳ አመንቴ በ 20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ በራሳቸው ጥረት ተምረው ሀገርን የማሻሻል ሀሳቦችን ያለመታከት ያቀርቡ ከነበሩት ምሁራን መካከል የወለጋ መሳፍንት ተወላጅ የሆኑት ፊታውራሪ በኋላ ብላታ ዴሬሳ አመንቴ ተጠቃሽ ናቸው።

ብላታ ዴሬሳ በዘመኑ የምሁራን መድረክ በነበረው ሳምንታዊው ብርሃን እና ሰላም ጋዜጣ ምናልባትም ከሁሉም የበለጠ ተከታታይ ጽሁፎችን ያቀረቡ ናቸው።

ብላታ ዴሬሳ አመንቴ በ 1935 ከወርሃ ጥቅምት እስከ ሰኔ መጨረሻ ድረስ ለዘጠኝ ወራት ያህል የመጀመርያው የሕግ መምሪያ ፕሬዚደንት ሆነው ተሾመው ሀገራቸውን በቅንነት አገልግለዋል።

ብላታ ደሬሳ በኢትዮጵያ የውጪ ጉዳይ ተልዕኮ ውስጥ ታላቅ ሚና የነበራቸው ፤ በንጉሡ ዘመን የገንዘብ እና ንግድ ሚኒስቴር እንዲሁም በአሜሪካን የኢትዮጵያ ተወካይ አምባሳደር ሆነው ያገለገሉት የአምባሳደር ይልማ ደሬሳ ወላጅ አባት ናቸው።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Jan, 16:19


ባህር ዳር ከተማ እና ገበያዋ

በ 1987 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

03 Jan, 18:17


➩ ክቡር አሰፋ ለማ
(በንጉሡ ዘመን የማዕድን ሚኒስቴር እንዲሁም በሀገረ ጀርመን የኢትዮጵያ አምባሳደር የነበሩ ፤ የክብርት ወ/ሮ ስንዱ ገብሩ ባለቤት)

➩ አንጋፋው ገጣሚና ሰዓሊ ገብረክርስቶስ ደስታ

➩ ሌፍተናንት ጄኔራል ከበደ ገብሬ
(በንጉሡ ዘመን የአገር መከላከያ ሚኒስትር የነበሩ ፤ የክብርት ወ/ሮ ደስታ ገብሩ ባለቤት)

(ከግራ ወደ ቀኝ)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

02 Jan, 19:29


#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Dec, 19:58


👇
youtu.be/TW3peVupAEI?si

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Dec, 16:20


ታህሳስ 6 ቀን 2009 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከዛሬ 8 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን አንጋፋው የህግ ምሁር አቶ ተሾመ ገብረማሪያም በተወለዱ በ 86 ዓመት ዕድሜያቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩበት ዕለት ነበር።

ሙሉ ታሪኩን
👇
www.facebook.com/share/v/15gZRzNnpt/

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Dec, 12:51


በወርሃ ታህሳስ 1953 ዓ.ም በተደረገው የመንግስት ግልበጣ ተከትሎ በወቅቱ በጋዜጣ ታትሞ የወጣው የይፈለጋሉ ማስታወቂያ ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Dec, 18:02


ክቡር ዶ/ር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠ እና
የ 1953 ዓ.ም መፈንቅለ መንግስት ኩነታ ታሪክ

የመፈንቀለ መንግስት ሙከራው በተካሄደ በአራተኛው ቀን መሰለኝ ጃንሆይ ጉብኝታቸውን አቋርጠው አዲስ አበባ ገቡ። አሁን አገር ሰላም ነው አልሁና እኖርበት ወይም በጭንቅ ሆኜ ሁኔታውን እከታተልበት ከነበረው ፊት በር እየተባለ ከሚጠራው ሰፈር ወጣሁና አራት ኪሎ አቶ ሻወል ቤት ገባሁ። ለካ ጦር ሰራዊት ይከታተለኛል። ድንገት ጀርባዬን በሰደፍ ደቅኖ ቀጥል አለኝ።

ከዛ ሌሎችም በጥፊ በርግጫ እያዳፋ እንዲያውም የሌለኝን መአረግ ሁሉ እየስጡኝ ''የኛ መቶ አለቃ! የሾሙህ የሸለሙህ ጃንሆይ መጥተዋል ምን ይዋጥህ? አንተ ከሀዲ! ለሰንደቅ አላማህና ለንጉስህ የገባህውን ቃል በልተህ መንግስት ልትገለብጥ ሞከርህ አይደል....''አሳሬን ያሳዩኝ ጀመር። መልስ ለመስጠትና ''መቶ አለቃ ቀርቶ ወታደር አይደለሁም ፤ ሲቪል ነኝ '' ብዬ ለመናገር እንኳ ፋታ አልሰጡኝም ቁም ስቅሌን አሳዩኝ።

ሙሉውን ታሪክ
👇

www.facebook.com/share/p/15e5vf2rAV

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Dec, 17:10


youtube.com/watch?v=TW3peVupAEI&si

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Dec, 17:07


ታህሳስ 4 ቀን 1953 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 64 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን በወንድማማቾቹ መንግሥቱ ንዋይ እና ገርማሜ ንዋይ የተጠነሰሰውና በተለምዶ "የታኅሣሡ ግርግር" በመባል የሚጠራው የመፈንቅለ መንግሥት ኩዴታ የተጀመረበት ዕለት ነበር።

#TariknWedehuala

youtube.com/watch?v=TW3peVupAEI&si

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

11 Dec, 14:00


👇
youtu.be/0rqPbplWY_k?si=uYDPTRtufgR1dp3N

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

11 Dec, 12:27


በ 40 ብር የአውሮፕላን ጉዞ

ከአዲስ አበባ ወደ ድሬዳዋ

በ 1981 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

11 Dec, 06:39


https://youtu.be/0rqPbplWY_k?si=qsauq-brWRwNs1vS

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

10 Dec, 15:48


አንጋፋዎቹ የጥበብ ፈርጦች (ከግራ ወደ ቀኝ)

➺ አርቲስት አስናቀች ወርቁ (የክራሯ ንግስት)

➺ ረዳት ፕሮፌሰር ሐይማኖት አለሙ

➺ አርቲስት ሶስና ዳንኤል

➺ አርቲስት ሐረገወይን አሰፋ

➺ ረዳት ፕሮፌሰር ተስፋዬ ገሠሠ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Dec, 20:19


ከ 52 ዓመት በፊት ህዳር 29 ቀን 1965 ዓ.ም ተሞክሮ የከሸፈው የአውሮፕላን ጠለፋ ላይ ተሳፋሪ የነበሩት አቶ አሰፋ አደፍርስ በወቅቱ ስለነበረው ሁኔታ ሲናገሩ ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Dec, 15:58


ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ለልጃቸው ልዕልት ተናኘወርቅ የፃፉላት ደብዳቤ

ከምወድሽ ልጄ ልእልት ተናኘወርቅ ኃይለሥላሴ ፤ ጤናሽን እንደም ነሽ ፤ እኛ ሥላሴ ይመስገን ደህና ነን ፤ ተማርሴይና ተፓሪ የጻፍሽው ደርሷል፤ እሮብ ከምርምሩ በኋላ ሃኪሙ የሚለውን እጽፋለሁ ያልሽውን እንጠብቃለን። ስለኛ እረፍት እንድናገኝ የጻፍሽው ከልብ እንድትአስቢ አውቃለሁ። ባይን የሚታየውን ለመለዋወጥ ካልሆነ አዲስ አበባ እንደፓሪስ ካልሆነች የሰው ደስታና ስራ ማየት ረዥም ህልም ማለት ነው። አንዳንድ ደስ የሚያሰኝ ፎተግራፍ ያገኘሽ እንደሆን እንድትልኪ ፤ ፒጃማ ፩ የሃር ፣ ፩ የጨርቅ ፣ ላይነት ጥሩ ከሚባለው ለኔ መጠን የሚሆን ገዝተሽ እንድትልኪ። እግዚአብሔር ያሰብነውን ቶሎ ያቃናልሽ ...

ሰኔ 14 ቀን 1941 ዓ.ም
ቀ.ኃ.ሥ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Dec, 14:46


ህዳር 29 ቀን 1965 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 52 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ መስመር ቁጥር 730 ቦይንግ አውሮፕላን 94 መንገደኞችንና 9 የበረራ ሰራተኞችን አሳፍሮ ከጥዋቱ አንድ ሰዓት ተኩል በአስመራ በኩል ወደ አቴንስ፣ ሮም ከዛም ወደ ፓሪስ ለመብረር ዝግጅቱን አጠናቆ በካፒቴን ቀጸላ አማካኝነት ምድርን ለቀቀ።

በወቀትቱ በአውሮፕላኑ ውስጥ ከነበሩት ተጓዦች መካከል ሰባቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም ሲሆኑ ፤ አውሮፕላኑ ከሰማዩ ገብቶ መብረር ሲጀምር ግን ያልታሰበ ሁኔታ ተከሰተ፡፡ እነዚያ ተማሪዎች አውሮፕላኑን በቁጥጥራቸው ስር ማዋላቸውን አስታወቁ፡፡ እነርሱ ወደሚፈልጉት ሀገር እንዲበሩም አብራሪዎቹን አዘዟቸው፡፡

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/1X2ePvUXxy

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Dec, 19:16


መስቀል አደባባይ በዘመኑ ፤

በ 1970ዎቹ -- አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Dec, 18:54


" አንጋፋ ሙዚቀኞች "

➺ ማህሙድ አህመድ (ድምፃዊ)

➺ መላከ ገብሬ (ቤዝ ጊታር)

➺ ዮሐንስ ተኮላ (ትራምፔት)

➺ ማህሙድ አማን (ጊታር)

➺ ተማረ ሃረጉ (ድራምና ፐርክሽን)

➺ ጌታቸው ካሳ (ድምፃዊ)

➺ ሃይሉ መርጊያ (ፒያኒስት)

➺ ግርማ በየነ (ሙዚቃ አቀናባሪና ድምፃዊ)

➺ ጥላዬ ገብሬ (ሙዚቃ ቅንብር)

➺ ውብሸት ፍስሃ (ድምፃዊ)

(ከግራ ወደ ቀኝ)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Dec, 18:12


በደርግ ዘመነ መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ ከአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ECA) መስሪያ ቤት ፊት ለፊት ቆሞ የነበረው የሩሲያዊው የኮሙኒስት አባት የቭላድሚር ሌሊን ሐውልት በሚፈርስበት ወቅት ፤

ሐሙስ ግንቦት 15 ቀን 1983 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Dec, 16:19


በኢትዮጵያ የሚኖሩትን የውጭ አገር ሰዎችን ያዋረደ ፣ የማይገባም ቃል የተናገረ እንደ ሕጉ በብርቱ ቅጣት ይቀጣል !!!

"የአዲስ አበባ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ለሕዝብ ማስታወቂያ"

ከዚህ ቀድሞ በመስከረም 11 ቀን 1928 ዓ.ም በተነገረው አዋጅ እንደሰማችሁት የኢጣልያ መንግሥት በኢትዮጵያ ላይ የአጥቂነት ሥራ በመሥራቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ከተነሣበት ጠላት እንዲከላከል ምንም ቢታዘዝ ጠላት የተባሉት ወሰን አልፈው መሣሪያ ይዘው የወገኖቻችንን የኢትዮጵያን ሰዎች ደም ለማፍሰስ የሚመጡ ኢጣልያኖች ናቸው እንጂ በአዲስ አበባ ከተማም ቢሆን ከከተማ ውጭም ቢሆን በኢትዮጵያ የሰላማዊነት ሥራ እየሠሩ ለመኖር የመጡት አይደሉምና የኢትዮጵያ ሕዝብ በእንግዳ ተቀባይነቱና በአክባሪነቱ ከውጭ አገር ሰዎች ጋራ ተስማምቶ በሳላም በመኖሩ በዓለም የተመሰገነ ስለሆነ ይህ መልካም ስማችን ሳይጠፋ ተከብሮ እንዲኖር ገፍቶ የመጣውን ጠላታችንን ወደድንበራችን ሒደን ለመመለስ ከማሰብ በቀር በመካከላችን እኛን ዘመድ አድርገው በሚኖሩ የውጭ አገር ሰዎች ላይ ማናቸውንም የጠላትነት አሳብ የሚገልጥ ነገር እንዳታደርጉ እናስታውቃለን። አሁን ከኢጣልያን ጋራ በተነሣው ጠብ ምክንያት በማስፈራራት በመጋፋት ወይም የማይገባ ቃል በመናገር ይህን በመሰለ አደራረግ ሁሉ በኢትዮጵያ የሚኖሩትን የውጭ አገር ሰዎች ያዋረደ፥ የማይገባም ቃል የተናገረ እንደ ሕጉ በብርቱ ቅጣት ይቀጣል።

መስከረም 14 ቀን 1928 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከንቲባ

ምንጭ:- ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Dec, 20:18


የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ አቶ መለስ ዜናዊ (ለገሰ)

በአድዋ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የንግሥተ ሳባ ት/ቤት ውስጥ በተዘጋጀው የተማሪዎች የክርክር ውድድር 1ኛ ወጥተው ባሸነፉበት ወቅት ሽልማታቸውን ከዓድዋ ገዢ ከደጃዝማች ኃይለሥላሴ እጅ ሲቀበሉ ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Dec, 18:54


➺ ድምፃዊ ጌታቸው ካሳ (ድራም የሚጫወተው)
➺ ድምፃዊ ግርማ በየነ (ፒያኖ የሚጫወተው)
➺ ካሜሮናዊው ማኑ ዲባንጎ (ሳክስፎን የሚጫወተው)
➺ ፒያኒስት ኃይሉ መርጊያ (ከኋላ ያለው)

አዲስ አበባ -- 1978 ዓ.ም
ሒልተን ሆቴል

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Dec, 16:34


የበረሃዋ ንግሥት ድሬዳዋ ከተማ እና የጎርፍ አደጋዎቿ ፤

በኢትዮጵያ ምስራቃዊ ክፍል የምትገኘው የበረሃዋ ንግስት ድሬዳዋ ከተማ በቀደምት ዘመኗ እና በቅርብ ጊዜያቷ በህዝቦቿና በከተማዋ ላይ ጥቁር ጠባሳ ትቶ ካለፉት የተፈጥሮ አደጋዎች መካከል የጎርፍ አደጋ አንዱ ሲሆን በወርሃ ሐምሌ 1998 ዓ.ም ከ 15 ዓመት በፊት የተከሰተው የጎርፍ አደጋ የቅርብ ጊዜያት ታሪክ ነው።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ከ 114 ዓመት በፊት በወርሃ ነሐሴ 21/22 ቀን 1900 ዓ.ም በከተሟዋና በአጎራባች ከተሞች ላይ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በከተማዋ ከባድ የጎርፍ አደጋ መከሰቱ ታሪኮች ይወሳሉ።

አንጋፋው የታሪክ ተመራማሪና ፀሐፊ የሆኑት ፕሮፌሰር ሪቻርድ ፓንክረስት ዘ ሶወር ኦፍ ኢትዮጵያ (The Sower of Ethiopia) ላይ ከመዘገቡት ዋና ዋና ክስተቶች መካከል በወቅቱ ስለ ጎርፉ አደጋ እንዲህ ብለው አስፍሯል።

"ከወትሮው በተለየ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በድሬዳዋ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ተከስቷል"።

Richard Pankhurst notes this kind of news in his record of the main events reported in The Sower of Ethiopia . As for example, August 27 and 28, 1908: “Because of the unusually heavy rains, there is a serious flooding in Dire Dawa.

➺ ከላይ የሚታዩት ፎቶግራፎች በከተማዋ ላይ በተለያየ ጊዜያት የተከሰቱ የጎርፍ ውሃ ፍሰት ሲሆኑ እያንዳንዱ ፎቶዎች ከመግለጫቸው ተቀምጧል።

#በዛሬዋ_ዕለት #TariknWedehuala@TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Dec, 13:00


የሕንድ ውቅያኖስን አቋርጠው እስያን በመጎብኘት የመጀመሪያው አፍሪካዊ ንጉሥ የሆኑት ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ ለይፋዊ ጉብኝት ሕንድ ቦምቤይ ግዛት ሲደርሱ የተደረገላቸው አቀባበል ፤

ጥቅምት 15 ቀን 1949 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

04 Dec, 13:00


ህዳር 25 ቀን 1560 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 457 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የዓፄ ልብነ ድንግል ሚስት የነበሩት እቴጌ ሰብለ ወንጌል አመድ በር በምትባል ሥፍራ ያረፉበት ዕለት ነበር።

የእቴጌ ሰብለወንጌል የአጤ ልብነድንግል ባለቤት የነበሩትና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ከፍ ያለ ቦታ ከያዙ እንስቶች መካከል ተጠቃሽ የሆኑት እቴጌ ሰብለወንጌል ያረፉት ከዛሬ 457 ዓመታት በፊት (ኅዳር 25 ቀን 1560 ዓ.ም) ነበር፡፡

በመጋቢት ወር 1521 ዓ.ም ሽምብራ ኩሬ ላይ በተደረገው ጦርነት አጤ ልብነድንግል ድል ከሆኑ በኋላ ንጉሡ በዐምሐራና በትግራይ አካባቢዎች እየተዘዋወሩ የግራኝ አህመድን ጦር ለመከላከል ሞከሩ፡፡

ይሁን እንጂ ለአንድ ጀንበር እንኳ ጥይት ድምፅ ተለይቶት የማያውቀው የሰሜናዊው/ደጋማው የክርስቲያን ግዛተ-አፄ (The Christian Highland Kingdom) ጦር በቱርኮች የጦር መሳሪያ እርዳታ የፈረጠመውን የግራኛ አህመድን ጦር መቋቋም ሳይችል ቀረ፡፡

ሙሉውን ታሪክ
👇
web.facebook.com/share/p/15Gsao3cUM/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Dec, 19:34


ህዳር 22 ቀን 1903 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከዛሬ 114 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያው የመድሐኒት መደብር (ፋርማሲ) ዶክተር ሜራብ በተባለ ፣ የጆርጂያ ተወላጅ የቅዱስ ጊዮርጊስ ፋርማሲ ወይም (Pharmacie la Géorgie) በሚል ስም ተሠይሞ የተከፈተበት ዕለት ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Dec, 18:00


የደራሲ ዳኛቸው ወርቁ 30ኛ የሙት ዓመት መታሰቢያ

ደራሲ፣ የሥነ-ጽሑፍ መምሕር፣ ገጣሚ እና የተውኔት ጠቢብ የነበረው ዳኛቸው ወርቁ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ከዛሬ 30 ዓመታት በፊት (ኅዳር 22 ቀን 1987 ዓ.ም) ነበር፡፡

ዳኛቸው የተወለደው ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን በወረረችበት፣ በ 1928 ዓ.ም ነው፡፡ አባቱ አውሮፓ ኖረው ስለነበር ለቀለም/ዘመናዊ ትምህርት ከፍ ያለ ግምት የሚሰጡ ሰው ነበሩ፡፡

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/1BewSDDBFo/

====////=====

#ታሪክን_ወደኋላ #በዛሬዋ_ዕለት #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Dec, 16:30


ደብረዘይት የአብራሪዎች ስልጠና ፤

በ 1951 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

22 Nov, 11:23


ህዳር 13 ቀን 1967 ዓ.ም

ከ 50 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ጊዜያዊ የወታደራዊው የደርግ መንግስት አባላት በቀድሞዎቹ የቀ.ኃ.ሥ ስልሳዎቹ ባለሥልጣናት እንዲገደሉ ውሳኔ የተሰጠበት ዕለት ነበር።

ለደርጉ የዘመቻና ጥበቃ መምሪያ መኮንን
አዲስ አበባ።

ጉዳዩ:- በቀድሞ የመንግሥት ባለሥልጣናት ላይ የተላለፈውን ከፍተኛ የፓሊሲ ውሳኔ ተግባራዊ ስለማድረግ ይመለከታል።

በአገራችን በፊውዳሉ አስከፊ ሥርዓት ላይ ተቀጣጠለውን ሕዝባዊ አብዮት መርቶ ከግቡ ለማዳረስ ግንባር ቀደም ኃላፊነቱን የወሰደው ከጭቁኑ መለዮ ለባሽ የተውጣጣው አብዮታዊ ደርግ የአገሪቱን ሥልጣን ተረክቦ በመምራት ላይ ይገኛል።

አብዮታዊ ደርግ ከተቋቋመበት ጊዜው ጀምሮ የዘውድ አገዛዝን ከማስወገድ አልፎ የ ቀ.ኃ.ሥ ባልስልጣናትን በቁጥጥር ስር አውሎ ጉዳያቸውን ሲያጠና የቆየ መሆን ከነዚህም መካከል ላለፉት 40 ዓመታት ጭቁኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ሲረግጡና ሲመዘበሩ የነበሩ ከፍተኛ የሲቪልና ወታደራዊ ባለስልጣናት ላይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውሳኔ አስተላልፏል።

ሰሞኑን የደርግ አባላት ባደረጉት ከፍተኛ ስብሰባ በአንደኛ ዙር የስም ዝርዝራቸው ከዚህ ትዕዛዝ ጋር የተያያዘው የቀድሞ ባለሥልጣናት ላይ አብዮታዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ሙሉው የደርግ አባላት በአንድ ድምፅ ወስኖዋል።

➺ ትዕዛዝ

1.ሌ/ጄ አማን አንዶም ከመኖሪያ ቤታቸው በቁጥጥር ስራ ውለው ወደ ቤተመንግስት በማምጣት ከእስረኛችን እንዲቀላቀሉ፣

2.በዋናው ከርቸሌ ለ 54 ሰው በዶዘር ጉድጔድ እንዲቆፈር ሆኖ ከተራ.ቁ 1 እስከ 54 ያሉት ከፍተኛ የሲቪልና የጦር ባለስልጣናት ከምሽቱ 2 ሰአት ከእስረኛች ተለይተው ለብቻ እንዲቆዩ

3. ከሌሊቱ 8:00 ሰዓት በወታደራዊ መኪናዎች ወደ ዋናው ከርቸሌ ተወስደው በአንድ ላይ በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ እናስታውቃለን

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Nov, 17:22


ህዳር 10 ቀን 1932 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 85 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን "የዘመናዊ ቴአትር ቤት" መሀንዲስ የሆኑት መራሔ ተውኔት አባተ መኩሪያ ከአባቱ ከአቶ ስለሺ ማንደፍሮ እና ከእናቱ ከወይዘሮ ውብነሽ መኩሪያ በአዲስ አበባ ከተማ አዋሬ ሠፈር ውስጥ የተወለዱበት ዕለት ነበር።

www.facebook.com/share/p/1LY3mS8o4V

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

19 Nov, 14:55


ፊታውራሪ ደስታ ፍሰሐ

የወላይታ ንጉስ የካዎ ጦና የልጅ ልጅ ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Nov, 17:14


ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ለማስመለስ ለሊግ ኦፍ ኔሽን ይግባኝ ለማለት ወደ ጄኔቫ በሚወሰደው በለንደን ቪክቶሪያ ጣቢያ ባቡር ሊሳፈሩ ሲሉ ሲሆን ፤ ከግርማዊ ጃንሆይ በስተኋላ የሚታዩት ልጆቻቸው ልዕልት ፀሐይ እና ልዑል መኮንን ኃይለሥላሴ ናቸው።

ሰኔ -- 1928 ዓ.ም ፤ ለንደን

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Nov, 16:52


የዓለም ሊቀ ሊቃውንት ፤ የኪነ ጥበብ ምሑር ፤

እጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ፤ በስራ ላይ

በ 1948 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

17 Nov, 19:24


ከታች በምስሉ ላይ የሚታየው ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ከስልጣን ከመውረዳቸው ከጥቂት ቀናት በፊት እንዲሁም የእርሳቸው የጥበቃ አዛዦች ከታሰሩ በኋላ የኢትዮጵያ ወታደሮች (ሠራዊቱ) በወቅቱ የነበረውን ስልጣን እና ኃይል ለማሳየት በአዲስ አበባ አውራ ጎዳናዎች ላይ ሲዘዋወር ፤

ነሐሴ 16 ቀን 1966 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

17 Nov, 19:00


ሶስት ቀን ከግማሽ የፈጀው የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የአስክሬን ፍለጋ ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

16 Nov, 16:30


ህዳር 7 1868 ዓ.ም

ከ 149 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት የዓፄ ዮሐንስ ሠራዊት ከግብጽ ጦር ጋር ጉንደት በተባለ ሥፍራ ላይ ጦርነት ገጥመው ድል የተቀዳጁበት ዕለት ነበር።

አፄ ዮሐንስ ከገጠማቸው ብዙ የውጭ ወራራ መካከልና የመጀመሪያው ወረራ የተቃጣባቸውም ከግብፅ ነበር፡፡ ግብፆች ይዞታቸውን ለቀው ወደ ደጋማው የኤርትራ ክፍል በገቡ ጊዜም፣ ንጉሰ ነገሥቱ በወቅቱ የግብፅ መሪ ለነበረው ለከዲቭ እስማኤል ‹‹አንተም ከአባቶችህ አትበልጥም፤ እኔም ከአባቶቼ አላንስምና፣ በየይዞታችን ሆነን በሰላማዊ ግንኙነት እንቀጥል›› ብለው መልዕክት ላኩበት፡፡

በተጨማሪም ንጉሱ ግብፅ የኢትዮጵያን ግዛት መድፈሯን ለወቅቱ የአውሮፓ ኃያላን መንግሥታት በተደጋጋሚ አስታውቀው ነበር፡፡ ከዲቭ እስማኤል ግን ሲመቸው በትዕቢት ሳይመቸው ደግሞ በማታለል የአፄ ዮሐንስ መልዕክትና ጥያቄ ሳይቀበል ቀረ፡፡ አውሮፓውያኑ መንግሥታትም የተዛባ መረጃ ስለደረሳቸው ይሁን ወይም ለገዛ ተንኰላቸው ሲሉ ለንጉሱ ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጡ ቀሩ።

ከዚህ በኋላ አፄ ዮውሃንስም ‹‹ኃይለኛ በሰራዊቱ ብዛት አይድንም፥ ፈረሰኛም በፈረሱ ጽናት አያመልጥም›› ብለው፣ ዐይናቸውን ወደ ሰማይ ሰቅለው ‹‹ሕዝብህን ከጥፋት አድን፣ ርስትህንም ባርካት፣ ለእኛ ለአገልጋዮችህ የማሸነፍን ኃይል ስጠን›› ብለው ጸልየው ወደ ጦርነቱ ጉዞ ጀመሩ፡፡

አቡነ አትናቴዎስም‹‹ጦርነቱ ቅዱስ ጦርነት ነው›› በማለት ወታደሩን ባረኩ፡፡ ጀግኖቹ የኢትዮጵያ ልጆችና ወራሪው የግብፅ ኃይልም ጉንደት ላይ ገጠሙ፡፡ ኢትዮጵያውያኑ አጥቂ ወራሪዎቹ ደግሞ ተከላካይ ሆኑ፡፡

የአፄ ዮሐንስ ጦር በራስ አሉላ እየተመራ ወራሪውን የግብፅ ጦር መፈናፈኛ አሳጣው፡፡ ግብፆች የጦር መሪያቸውን ለሞት አሳልፈው ሰጥተውና ሙሉ በሙሉ ተሸንፈው ከሞት የተረፉት ሸሽተው ተበታተኑ፡፡

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Nov, 17:57


የኤርትራ የነጻነት ህዝበ-ውሳኔ ምርጫ (ሪፈረንደም) በተደረገበት ዕለት ፤

(ሚያዝያ 15/17 1985 ዓ.ም)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Nov, 17:29


ይህ የባይተዋሩ የልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ የነሐስ ቅርፅ ከህልፈቱ በኋላ በንግስት ቪክቶሪያ ትዕዛዝ ተሰጥቶ እ.ኤ.አ በ 1879 የተሰራ ሲሆን የተቀረፀውም በእንግሊዛዊው የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያ ፍራንሲስ ጆን ዊሊያም ሲሆን እ.ኤ.አ በሐምሌ 1880 በዊንዘር ቤተመንግስት ሰን ስራውን ጨርሶ አስረክበዋል።

የዚህ የልዑል ዓለማየሁ ቅርፅ ወደ ንግሥት ቪክቶሪያ ተወዳጅ መኖሪያ (Osborne House) ኦስቦርን ሃውስ ውስጥ በላይኛው ኮሪደር እንዲቀመጥ ተደርጓል።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Nov, 16:13


ቀደምት የነገሥታት እና የመሪዎች የፈረስ ስም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

14 Nov, 15:20


ህዳር 5 ቀን 1872 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 145 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ዕለት የዳግማዊ ዓፄ ቴዎድሮስ እና የእቴጌ ጥሩወርቅ ውቤ ልጅ ፣ ልዑል ዓለማየሁ ቴዎድሮስ በስደት ከሚኖሩበት እንግሊዝ አገር ከ 12 ዓመት ቆይታ በኋላ በተወለደ በ 19 ዓመቱ ባደረበት የሳምባ ምች ሕመም ምክንያት ህይወቱ ያለፈበት ዕለት ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Nov, 16:45


ናዝሬት ከተማ በዘመኗ ፤

"ግንብ ገበያ"

(1938 -- 1943 ዓ.ም)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Nov, 15:15


ህዳር 4 ቀን 1924 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከዛሬ 93 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን በኢትዮጵያ በውጭ ጉዳይ ዙሪያ ትልቅ ተሳትፎ ያደረጉት ስመጥሩ የፖለቲካው ሰው ራስ ናደው (አባ ወሎ) ህይወታቸው ያለፈበት ዕለት ነበር

ራስ ናደው አባ ወሎ በፈረስ ስማቸው “አባ መብረቅ” በዳግማዊ ምንሊክ ዘመነ መንግሥት እና በንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ዘመነ መንግሥት በተለይም በውጭ ጉዳይ ዙሪያ ትልቅ ተሳትፎ የነበራቸው ስመጥር የፖለቲካ ሰው ነበሩ።

ራስ ናደው ትውልዳቸው በሰሜን ሸዋ ታዋቂ እና ተጽዕኖ ፈጣሪ ከሆነው ከአዲስጌ ቤተሰብ ነው። ራስ ናደው አባ ወሎ በውጪ ጉዳይ በነበራቸው ከፍተኛ ተሳትፎ ባሻገር ለረዥም ጊዜ የኢሉባቦር ግዛት (ገዢ) በመሆን አስተዳድረዋል።

በውጪ ጉዳይ ዙሪያ በነበራቸው ተሳትፎ በንግሥት ዘውዲቱ ዘመን ከ 1ኛው የዓለም ጦርነት ብኋላ በአሸናፊነት የወጡትን የተባበሩት ኃይል እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ወደ አውሮፓና አሜሪካ የሂደውን የኢትዮጵያ ልዑክ መርተዋል።

በዚህ ጉዞ በራስ ናደው የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ዩናይትድ ኪንግደምን እና አሜሪካን የጎበኘ ሲሆን እግረ መንገዱንም የኢትዮጵያን ልዑላዊነትና በዓለም አቀፍ ፖለቲካው ያላትን ቦታ ለዓለም አስረድቷል። ኢትዮጵያ ወደ ሊግ ኦፍ ኔሽንስ ለመግባት ጥረት በምታደርግበት ወቅት ራስ ናደው የኢትዮጵያ ወኪል ሆነው አገልግለዋል።

ለዚሁ ጉዳይ ወደ ጄኔቫ የሄደውን ቡድን የመሩም ሲሆን ቡድኑ ከራስ ናደው በተጨማሪ ብላቴን ጌታ ኃሩይ ወልደሥላሴና ፋሲካን በመልዕክተኝነት የያዘ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ራስ ተፈሪ መኮንን (በኋላ አፄ ኃይለላሴ) ወደ አውሮፓ ባደረጉት ጉብኝት አጅበው ከሄዱት ሰዎች መካከል ራስ ናደው አባ ወሎ አንዱ ነበሩ።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

10 Nov, 18:37


https://youtu.be/DNVFIh-P0aE?si=5FPIvcsBk1aVuGvx

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

10 Nov, 18:29


አንጋፋው ጋዜጠኛ ዜናነህ መኮንን

(1945 -- 2017)

https://youtu.be/DNVFIh-P0aE?si

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

10 Nov, 17:16


ባለወርቃማ ድምፁ ዜና አንባቢና ደራሲ ዜናነህ መኮንን በተወለደ በ 72 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

አንጋፋዎቹ መገናኛ ብዙሀን የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን በ70ዎቹ እና 80ዎቹ ሲታወሱ ዛሬም ድረስ ስሙ በጉልህ ይነሳል። የታሪክ ተመራማሪ፣ የመካከለኛው ምስራቅ የፖለቲካ ተንታኝ የጀርመን ድምፅ ሬዲዮ ልዩ እና ተወዳጅ ዘጋቢ ነዉ፡፡

ዜናነህ መኮንን ከጋዜጠኛነቱ በተጨማሪ ደራሲ፣ ገጣሚና ሃያሲም ነው። ከግርማ ሞገሱ ጋር ግርማ ሞገስን የሚያላብስ ልብስ ለብሶ በኢትዮጲያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሸቱ ሁለት ላይ “ጤና ይስጥልኝ እንደምን አመሻችሁ ከሰዓቱ ዜና ጋር ዜናነህ መኮንን ነኝ” በማለት እጅ ሲነሳ የብዙዎች ትዝታ ሆኖ አልፏል።

በበርካታ የቲቪ እና የሬድዮ ተከታታዮች ዘንድም የሚወደድ ነው፡፡ የጀርመን ድምጽ (ዶቼ ዌሌ ሬዲዮ) የጣቢያው መክፈቻና መዝጊያ ድምፅ የዚሁ አንጋፋ ጋዜጠኛ ነው፡፡ ይህ ሰዉ ኑሮውን በእየሩሳሌም ካደረገ ዘመናት ተቆጥረው ነበር።

ውልደት እና እድገት

ዜናነህ በ1945 ዓ.ም ጎንደር አዘዞ በምትባል ከተማ ውስጥ መስከረም ወር ላይ አደይ አበባና አዲስ አመቱን ተከትሎ ነበር ወደዚህች ምድር የመጣው። ውልደቱ አዘዞ ይሁን እንጂ በ ቤተሰቦቹ የሥራ ፀባይ ምክንያት ወደ አዲስ አበባ የመጣው በልጅነቱ ነበር፡፡ በመቀጠልም ወደ ጂማ ሄዶ “ቆጪ” ሰፊር ይኖሩና ፃዲቁ ዮሀንስ (አሁን የመምህራን ማሠልጠኛ ተቋም ሆኗል) ይማር ነበር፡፡

ጂማ እስከ 3ተኛ ክፍል ድረስ ከተማረ በኋላ ወደ ጎንደር በመሄድ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን ጨርሶ የሁለተኛውንም አጋምሷል።....

ሙሉውን ታሪክ
👇

https://www.facebook.com/share/p/1BFhVajoaY/

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

09 Nov, 10:36


የጅቡቲው ፕሬዝዳንት ሀሰን ጉሌድ ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ ወደ ኢትዮጵያ በመጡበት ወቅት ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም እና ባለቤታቸው ወ/ሮ ውብባንቺ ቢሻው አቀባበል ሲያርጉላቸው ፤

መጋቢት 9 ቀን 1973 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

09 Nov, 10:06


ጥቅምት 30 ቀን 1848 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከዛሬ 169 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የሸዋ ንጉሥ ሳህለሥላሴ ወሰንሰገድ እና የወይዘሮ በለጥሻቸው ወልዴ ልጅ የሆኑት ንጉስ ኃይለመለኮት ሳህለ ሥላሴ በድንገተኛ ኅመም ምክንያት አርፈው በደብረ በግዕ የተቀበሩበት ዕለት ነበር።

የሸዋው ንጉሥ ኃይለመለኮት በሰውነታቸው ግዝፈትና ጥንካሬ እንዲሁም በልባቸው ቀናነት በሸዋ ዘንድ የታወቁና የተወደዱ ንጉሥ ነበሩ። ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ የኢትዮጵያ ታሪክ በሚለው መጽሐፋቸው እንደሚነግሩን ንጉሥ ኃይለመለኮት ከጥንካሬያቸው የተነሳ ኢላማ ተኩስ በሚተኩሱ ጊዜ መሳሪያውን አጠንክረው በመያዛቸው ምክንያት ጥይቱ ሲወጣ ጠምንጃቸው ለሁለት ተሰብሮ እጃቸው ላይ ቀርቶ ያውቃል።

ንጉሥ ኃይለመለኮት ከአባታቸው ሞት በመቀጠል ወደንግሥናው ዙፋን ከወጡ በኋላ ሸዋን ለ 8 ዓመታት አስተዳድረዋል። በስልጣን ላይ ሳሉም ተቀናቃኝ ሊሆኑባቸው የሚችሉትን ወገኖቻቸውን በእስር ዞር እንዲያረጓቸው ከጓናቸው ያሉ ሰዎች ሲመክሯቸው "ተዉ ይሄን አላደርገውም እግዚአብሔር የወደደውን ነው የሚያስገዛው" የሚሉ ቀና እንደነበሩ ብላቴን ጌታ ኅሩይ ወልደሥላሴ በመጽሐፋቸው ይጠቅሳሉ።

በመጨረሻም አጼ ቴዎድሮስ በሀገሪቱ በየቦታው ያለውን የተከፋፈለ አገዛዝ ወደ አንድ በማምጣት በማእከላዊ መንግሥት ስር የምትተዳር አንዲት ሀገር ለመመስረት አስበው ከየመሳፍንቱ ጋር በሚዋጉ ጊዜ ወደ ሸዋም ሊመጡ ነው የሚል ወሬ ተሰምቶ ንገሥ ኃይለመለኮትም ለጦርነት ተዘጋጁ፤ ሆኖም ግን ገና ቀደም ብሎ ንጉሡ ኃይለመለኮት በጣም ታመው ነበርና እርሳቸው በጦርነቱ ሳይካፈሉ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩት ንጉሥ ኃይለመለኮት ሳህለሥላሴ የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ አባት ናቸው።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Nov, 19:44


በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የሴት ትራፊክ ፖሊስ በሥራ ውላለች ግን አንዳንድ ባለመኪኖች ማሽገጠጥ ጀምረዋል። ትናት ማታ ገደማ የሴት ፖሊስን ትዕዛዝ ባለመፈፀም ያሽገጥጣት የነበረው የጂፑ ሹፌር ነው.......

ታህሳስ 17 ቀን 1960 ዓ.ም
(አዲስ ዘመን)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

08 Nov, 18:48


በሀገራችን የተደረገው 3ተኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ፤

ሐምሌ -- 1957 ዓ.ም

አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Nov, 20:07


ጀግናዋ አርበኛ ሸዋነሽ አብረሃ

ወይዘሮ ሸዋነሽ አብረሃ በጣሊያን ወረራ ዘመን ጠላትን በቆራጥነት የተዋጉ ሴት አርበኛ ናቸው። አባታቸው ደጃዝማች አብረሃ አርአያ የዘር ሀረጋቸው ከ አጼ ዮሐንስ አራተኛ ይመዘዛል። ባለቤታቸው ደጃዝማች ኃይሉ ከበደ በዋግ የታወቁ የአርበኛ መሪ ነበሩ።

በ1929 ዓ.ም ደጃዝማች ኃይሉ ሲሰው እና የዋግ አርመኞች ላይ ዘግናኝ የሆነ ፍጅት ሲፈጸም ወ/ሮ ሸዋነሽ በህይወት የተረፉትን አርበኞች አስተባብረው ወደ በጌምድር በመሻገር በልጆቻቸው ደጃዝማች ተፈራ ተሰማ እና ልጅ (ብኋላ ዋግሹም) ወሰን ኃይሉ እየታገዙ ትግሉን ቀጠሉበት።

ወይዘሮ ሸዋነሽ ትግላቸውን ለማጠናከር ከተለያዩ የአርበኛ መሪዎች ጋር ግንኙነት ይፈጥሩ ነበር። በዚህም መሰረት በበጌምድር ለታወቀው የአርበኛ መሪ ልጅ ዮሐንስ ኢያሱ (የልጅ ኢያሱ ልጅ) ልጃቸውን ዘውዲቱን በመዳር ዝምድናን ፈጥረዋል። ያም ሆኖ አልፎ አልፎ በአርበኛ መሪዎቹ መካከል የእኔ በልጥ እኔ በልጥ ግጭቶች እየተነሱ ትግሉን እንቅፋት ይፈጥሩበት ነበር።

ግርማዊ ቀዳማዊ ዐፄ ኃይለሥላሴ ጎጃም በደረሱ ጊዜ ወይዘሮ ሸዋነሽ አብረሃ ልጃቸው ወሰን ኃይሉ ንጉሡን እንዲያገኝ ልከው እሳቸው ወታደሮቻቸውን አስተባብረው ዋግን ነጻ ለማውጣት ዘመቱ። የዋግ አርበኞች በራስ ስዩም መንገሻ እየተመሩ ሚያዚያ 20 ቀን 1933 ዓ.ም ሰቆጣን ተቆጣጠሩ። የወወይዘሮ ሸዋነሽ ወታደሮች አምባላጌ ላይ በተደረገው ጦርነትም ተሳታፊ ነበር።

ከድል ብኋላ ለአርበኛ ሸዋነሽ አብረሃ ለፈጸሙት ጀግንነት የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳሊያዎች ተበርክተውላቸዋል።

ክብርና ሞገስ ለጀግናዋ አርበኛ ሸዋነሽ አብረሃ 🙏

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Nov, 18:42


ጥቅምት 27 ቀን 1929 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 88 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን በአድዋ ጦርነት ጀግንነታቸው ያስመሰከሩት እንዲሁም በ 2ተኛው የኢትዮ ኢጣሊያን ጦርነትም ወቅት በእርጅና ዕድሜያቸው ዳግም የዘመቱት ጀግናው አርበኛ ደጃዝማች ባልቻ ሳፎ (አባ ነፍሶ) በተወለዱ በ 75 ዓመታቸው አቤቤ በተባለ ቦታ በኢጣሊያ ጦር ተመትተው ህይወታቸው ያለፈበት ዕለት ነበር።

*

ደጃዝማች ባልቻ አባ ነፍሶ ነጻ በወጣው የመቀሌ ምሽግ ላይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ስለመስቀላቸው እና የጣሊያን ሰራዊት ከመቀሌ ምሽጉ ስለመባረሩ

........እቴጌ ጣይቱም ሰራዊታቸውን እንዲህ ብለው አዘዙ፣

ከጉድባው ገብተን ካልተዋጋን ብላችሁ ብትመኙም ለብዙ ሰራዊት ትንሽ ጉድባ አይበቃውምና ከጣሊያን ሰራዊት ይልቅ እናንተው እርስ በርስ ተታኩሳችሁ ታልቃላችሁ፡፡ ከጉድባው ሄደን ካልተዋጋን የምትሉ ሰዎች ሜዳው ላይ ሆናችሁ ጣሊያን ውሃ እንዳይቀዳ ለማድረግ እንደማትፈሩ ተስፋ አደርጋለሁ።

ሙሉውን ታሪክ
👇

www.facebook.com/share/1293jsTUSoD/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Nov, 17:49


እጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት ሜትር

አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Nov, 17:29


የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ጓድ መንግሥቱ ኃይለማርያም (ሌ/ኮ) በሞስኮ ጉብኝት ሲያደርጉ ፤ ህዳር 7 ቀን 1971 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

06 Nov, 16:35


https://youtu.be/fZGXKcm3eHg?si=lCjlN042yPqeVcYL

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

05 Nov, 15:42


https://youtu.be/69UzW8NodMc?si=boUjHd_qwW80mr4U

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

03 Nov, 17:46


የመጨረሻው የወላይታ ንጉስ ካዎ ጦና ጋጋ የልጅ ልጆች:-

➺ ወይዘሮ አየለች አላየህ (በግራ)

➺ ወይዘሮ እልፍነሽ አላየህ (በቀኝ)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

03 Nov, 17:16


የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዶክተር ምናሴ ኃይሌ በአዲስ አበባ የተደረገው የተባበሩት መንግስታት የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ንግግር ሲያደርጉ ፤

ግንቦት 1964 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

02 Nov, 14:07


ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ

ሐረር ቤተመንግሥት ፤

1961 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

02 Nov, 10:25


ጥቅምት 23 ቀን 1923 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 94 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ልዑል አልጋ ወራሹ ንጉሥ ተፈሪ መኮንን በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን የንጉሠ ነገሥትነት ዘውድ ጭነው ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የተባሉበት ዕለት ነበር።

ንግስተ ነገስት ዘውዲቱ መጋቢት 22 ቀን 1922 እንዳረፉ ፤ ስልጣኑን የተረከቡት ተፈሪ ከሰባት ወር በኋላ ጥቅምት 23 ቀን 1923 ዓ.ም ነበር የስርዓተ-ንግስ በዓላቸው በደማቅ ሁኔታ የተከናወነው፡፡

እነዚያ 7 ወራት በኢትዮጵያ ምድር ታይቶ የማይታወቅ የበዓል ማሸብረቂያ ዝግጅት የተካሄደባቸው ናቸው ፥ ንጉሠ ነገሥቱና እቴጌዋ የሚጓዙበት ሠረገላ ከጀርመን አገር መጣ ፥ ልብሱ ሁሉ በወርቅና በሐር የተሽቆጠቆጠ ነበር፡፡ የአዲስ አበባ ክርንክስ ቤቶች እንዲወገዱ ተደረገ ፥ መንገዱ አስፋልት ሆነ፡፡

ሙሉውን ታሪክ
👇
www.facebook.com/share/p/J1pYEP3ozdb4zXPL/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Nov, 18:38


ጥቅምት 22 ቀን 1923 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 94 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የንግሥ በዓል ዋዜማ ፤ የንጉሠ ነገሥት የዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ሐውልት በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አጠገብ ፤ ለበዓል የመጡት እንግዶች በተገኙበት ሥርዐት፣ የሐውልቱን መጋረጃ የመግለጥ ክብር ለብሪታንያ ንጉሥ ወኪል ለ (ዱክ ኦፍ ግሎስተር) ተሰጥቶ ሐውልቱ የተመረቀበት ዕለት ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

01 Nov, 18:34


https://youtu.be/lor9HjgKY5A?si=pi8leBkwx0YrJh7X

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

31 Oct, 20:00


https://youtu.be/Qn4OFZcEKQ0?si=HHBtLTsgfpzkMVKN

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

31 Oct, 14:12


ራስ ብሩ ወልደገብርኤል

ራስ ብሩ ለአፄ ምኒልክ ስመጥር መኳንንት አንዱ ከሆኑት ደጃች ወ/ገብርኤል በ 1882 ዓ.ም ተወለዱ። ደጃ. ወ/ገብርኤል ከሚኒልክ ጋር በነበራቸው ልዩ ቀረቤታና ታማኝነት ሳቢያ እርሳቸው ሲሞቱ ልጃቸው ከልዑላን ጋራ በታላቁ ቤተ መንግስት ውስጥ አደጉ።

በዚህም ለምሳሌ ራስ ብሩ በልጅነታቸው በቤተመንግስት የግብር አመጋገብ ደረጃቸው ከልጅ ኢያሱ ሚካኤል፣ከራስ ተፈሪ (በኋላ አፄ ኃይለስላሴ) እና ከራስ ጌታቸው አባተ ቧያለው ጋር የተስተካከለ ነበር።

ራስ ብሩ የራስ ማዕረግ እስከሚያገኙ ድረስ በአገሪቱ ጦር ውስጥ ከፍተኛ ስም አትርፈዋል። በማይጨው ከባድ ተጋድሎ ያደረጉ ጀግና መሪም ነበሩ። የጦር ሚኒስትር ሆነውም አገልግለዋል።

ራስ ብሩ በአለባበሳቸው ሽቅርቅርና ስልጡን መስፍን ነበሩ። መኪና ትራንስፖርት ከመጣ በኋላ እርሳቸው በመኪና እየሄዱ በፈረስ ይታጀቡ ነበር።

ራስ ብሩ ሰፊ ሀብት የነበራቸው ቱጃር መስፍን ነበሩ። ሌላው የራስ ብሩ መለያ ለጋስነታቸው ነው። በዘመኑ የራስ ብሩን ያህል ግብር የሚያበላ መስፍን አልነበረም። 'ግብርስ እንደ ራስ ብሩ’ ይባልላቸውም ነበር።

የራስ ብሩ ወ/ገብረኤል መኖሪያ ቤታቸው ከመስቀል አደባባይ ከፍ ብሎ ኮረብታው ላይ ጎልቶ የወጣው ህንጻ ነው። ህንፃው የህንዶች የኪነ-ህንጻ አሻራ ያረፈበትና በ 1912 ዓ.ም ገዳማ የተሰራ ሲሆን የራስ ብሩን ዘመናዊ ቤት አሰራር የተመለከቱ በርካቶች መሳፍንትና መኳንንት የእርሳቸውን አርዓያነት በመከተል የውጭ አገር መሀንዲሶች እየከፈሉ ዘመን ተሻጋሪ ቤቶችን አስገንብተዋል። የመስቀል ደመራ በዓል ማክበሪያ ቦታም መጠሪያ ስሙ ራስ ብሩ ሜዳ ይባል ነበር።

➺ ከታች በምስሉ ላይ የሚታዩ ራስ ብሩ ፎቶ የተነሱት የደጃዝማች ማዕረግ በነበሩበት ወቅት ነበር።
#rare#photo

#ታሪክን_ወደኋላ

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

29 Oct, 19:43


የመጀመሪያዎቹ 7ቱ የግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ የካቢኔ ሚኒስትር ተሿሚዎች ፤

ግንቦት 2 ቀን 1933 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

29 Oct, 17:05


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፎች

በ 1961 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

29 Oct, 15:34


በቀዳማዊ ኃይለሥሳሴ ዘመን እንግሊዝም ከኢትዮጵያ ምፅዋት ተቀብላ ነበር።

ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ንጉሠ ነገሥት ዘ ኢትዮጵያ በክረምቱ በዘነበው ኃይለኛ ዝናብ ምክንያት ጉዳት ለደረሰበት አገር ለእንግሊዝ እርዳታ ገንዘብ ልከው ነበር። ይህም እርዳታ በሌጋሲዮኑ በኩል ሲላክ ቀጥሎ ያለው ደብዳቤ አብሮ ተልኳል፡፡

ለክቡር ሚዬሪክናሺ ናልዲስትሬስ ሎንዶን:-

“ምንም እንኳን እኛም ራሳችን በሕዝባችን ላይ ያለ አግባብ በግፍ የደረሰበትን ጉዳት በማቃለል ሥራችን ላይ ብንሆንም ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቀው ኃይለኛና ጨካኝ በሆነው ክረምት ምክንያት ሁልጊዜ በምናስባት ለምለምና ውብ በሆነች አገርዎ ላይ ለደረሰው ጥፋት መጠነኛ የገንዘብ እርዳታ መጠየቅዎን ስለሰማን የገንዘቡ ቁጥር ምንም ከፍ ያለ ባይሆንም የኛንና የሕዝባችንን እርዳታ ለመግለፅ ያህል አንድ ሺህ ፓውንድ በሌጋሲዮናችን በኩል ልክንልዎታል።

(ብርሃንና ሰላም መጽሔት 1946 ዓ.ም)

በስምግባር የታነፀችና ሃይኖራት የምትቸር የትንሽ ትልቅ የሆነች ውድ እትዮጵያንን ውለታዋን እየረሱ በየታሪክ አጋጣሚው የታላላቅ አገሮች ወይም የእንግሊዝና ተፅዕኖ የማይለያት ለመሆኗ ባለፈው ወር የጣሉባትን ማዕቀብ ማስታወስ ይገባል።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

29 Oct, 13:14


የመከላከያ ሚኒስትር ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህንፃዎች አጠቃላይ ዕይታ ፤

ነሐሴ -- 1960 ዓ.ም
አዲስ አበባ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

29 Oct, 09:28


የኢትዮጵያ የመከላከያ ሚኒስትር የነበሩት ሌተናል ጄነራል መርዕድ መንገሻ ከባለቤታቸው ከወይዘሮ ገበያነሽ ኃይለ ሥላሴ ጋር ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

©️ Solomon Zenah-bezu Messai

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

28 Oct, 19:33


ሰኔ 1987 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ላይ በተዘጋጀው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት የመሪዎች ጉባኤ ላይ የመክፈቻ ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ የአፍሪካ መሪዎች ወደ ከተማዋ የመጡበት ወቅት ነበር። ከተገኙት መሪዎች መካከል አንዱ የግብፅ ፕሬዝዳንት ሆስኒ ሙባረክ ናቸው።

ሆኖም በዕለቱ ያልታሰበ ከባድ ነገር በከተማዋ ላይ ተፈጠረ፤ ክስተቱም በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ፕሬዝዳንት ሆስኒ ከአዲስ አበባ አየር ማረፊያ ተነስተው ወደ ጉባኤው በሚሄዱበት ወቅት ከአውሮፕላን ማረፊያ በቅርብ ርቀት በሚገኘው የፍልስጤም ኤምባሲ አቅራቢያ 2 ተሽከርካሪዎች ወደ ዋናው መንገድ በመግባትና መንገዱን በመዝጋት ኤኬ-47 የተባለውን መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች ከተሽከርካሪዎቹ ወጥተው ፕሬዝዳንቱን ለመግደል ቶክስ የከፈቱበት ሙከራ ነበር።

ከዚያም የሙባረክ የፕሬዚዳንታዊ ጥበቃዎችና የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች በሽብርተኞቹ ላይ የመልስ ምት የተኩስ ጥቃት በወሰዱት እርምጃ 2 ወዲያውኑ ሲገደሉ 1ኛው በከባድ ቆስሏል።

በሁኔታው አስገራሚው ነገር የነበረው በወቅቱ ፕሬዝዳንቱ ላይ ምንም አይነት ጉዳት ሳይደርስባቸው በህይወት መትረፋቸው ነው።

"በድንገት አንድ መኪና ከፊታችን መንገዱን ዘግቶ ቆመ! ከዚያም ከውስጡ አንድ ሰው ወጥቶ ወደ እኛ መተኮስ ጀመረ። የተኮሱብኝን በሚገባ አይቻቸዋለሁ" (ፕሬዝዳንቱ ስለተፈጠረው ሁኔታ የተናገሩት)

ከላይ በምስሉ ላይ በወቅቱ ፕሬዝዳንቱን ለመግደል የሞከሩት ታጣቂዎች የተጠቀሙበት ተሽከርካሪ መኪና፣ ለጥቃቱ አላማ ታስቦ ሊውል የነበረው የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችና በኢትዮጵያ ፖሊስ በተያዘበት ወቅትና ስለጥቃቱ (The Ethiopian Herald) በሰኔ 20/ 1987 የፊት ገፁ ላይ ያወጣው እትም ምስል ናቸው።

#ታሪክን_ወደኋላ

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

28 Oct, 12:31


የዳግማዊ ዐፄ ምኒልክ ቤተመንግሥት

በዘመኑ የነበረው ገፅታ ፤ 1909 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

28 Oct, 11:54


የጎንደር ገበያ በዘመኑ ፤

ግንቦት -- 1907 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

24 Oct, 20:41


ልዑል መኮንን ኃይለ ሥላሴ (መስፍነ ሐረር) ህይወታቸው ያለፈው ምክንያት በመኪና አደጋ ስለመሆኑ ምስክርነት ሲሰጡ ፤

(ግንቦት 24 ቀን 1949 ዓ.ም)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

24 Oct, 20:36


ጥቅምት 14 ቀን 1900 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከዛሬ 117 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን በሀገራችን የዘመናዊ የመንግስት አስተዳደር ስርዓት ካመጡት መሪዎች አንዱ የሆኑት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የሚኒስቴር መስሪያ ቤት በማቋቋም እና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያዎቹ ለዘጠኙ ሚንስትሮቻቸው ሾሙት የሰጡበት ዕለት ነበር።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

22 Oct, 18:44


ኢትዮጵያ የወገንና የቡድን መከፋፈል የሚያስፈልጋት አይደለችም፡፡ ዛሬ የምናገረው ፤ እንደ እያንዳንዳችሁ እንደ አንዱ ኢትዮጵያዊ ሆኜ ነው፡፡ አንድ ግብ ብቻ ነው ያለን - ኢትዮጵያ፡፡ አንድ መተባበሪያ ዓላማ ነው ያለን - ኢትዮጵያ፡፡ አንድ ፕሮግራም ብቻ ነው ያለን ኢትዮጵያ፡፡

ፀሐፊ ትዕዛዝ ክቡር አቶ አክሊሉ ሀብተወልድ
ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው በተሾሙበት ዕለት ያደረጉት ንግግር (ሚያዝያ -- 1958 ዓ.ም)

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

22 Oct, 16:59


በእጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት ሜትር አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ የተሳለው የኢትዮጵያዊቷ ሴት (ወ/ሮ እሌኒ አብርሃም) ምስል ፤

የተሳለው በ 1947 ዓ.ም ፤ ሮም ከተማ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

22 Oct, 16:26


ጥቅምት 12 ቀን 1923 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 94 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን አንጋፋው ደራሲ ፣ ጋዜጠኛ ፣ ተርጓሚና ገጣሚ አቶ ማሞ ውድነህ በቀድሞው የወሎ ክፍለሃገር በዋግ አውራጃ ዐምደ ወርቅ ከተማ ውስጥ የተወለዱበት ዕለት ነበር።

ደራሲና ጋዜጠኛ ማሞ ውድነህ ከአባታቸው ከአቶ ውድነህ ተፈሪ እና ከእናታቸው ወይዘሮ አበበች ወልደየስ በወርሃ ጥቅምት 12 ቀን 1923 ዓ.ም በዋግ አውራጃ ዐምደ ወርቅ ከተማ ተወለዱ።

ገና በልጅ እድሜያቸው ወላጆቻቸውን በአምስቱ አመት የጣሊያን ወረራ ጊዜ ነበር ያጡት። ማሞ ውድነህ 12ኛ ክፍልን ያጠናቀቁት ገና በ15 ዓመት እድሜያቸው መሆኑ በጊዜው ተደናቂ ወጣት አድርጓቸው ነበር።

👇 ሙሉውን ታሪክ

www.facebook.com/share/p/Pw9i8FE6rSRXBcqW/

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

22 Oct, 15:21


https://youtu.be/dFJD5v9S73w?si=O-kI7EtrgbDDwwLd

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

20 Oct, 20:11


108 መንገደኞችን አሳፍሮ የነበረውን የሶማሊያ አውሮፕላን የጠለፉት 5 ታጣቂዎች አዲስ አበባ አየር ማረፊያ የነበራቸው የድርድር ሂደት ፤
ህዳር - 1977 ዓ.ም
👇👇👇

https://youtu.be/5ubZL8aHaZY?si=OnxADULJOoWE_Mgt

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

20 Oct, 16:47


በመዲናዋ አዲስ አበባ የሚገኙ ተማሪዎች የፈንጣጣ በሽታ የመከላከያ ክትባት ለመከተብ በአዲስ አበባ ስታዲየም ውስጥ ተሰብስበው ይታያሉ ፤

ህዳር -- 1967 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

20 Oct, 09:35


ጥቅምት 10 ቀን 1961 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 56 ዓመታት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ጀግናወሰ ኢትዮጵያዊው አትሌት ሻምበል ማሞ ወልዴ በሜክሲኮ ኦሊምፒክ የማራቶን ውድድር ላይ 2:20:26 ሰዓት በመግባት ለሀገሩ 🥇የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘበት ዕለት ነበር።

አትሌት ሻምበል ማሞ ወልዴ በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ታሪክ በአንድ ኦሊምፒክ ሁለት ሜዳሊያ ያገኘ ቀዳሚው አትሌት ነው። ከማራቶን ድሉ አንድ ሳምንት በፊት በ 10 ሺሕ ሜትር በኬንያዊው ናፍታሊን ቴሙ በሽርፍራፊ ሴኮንዶች ተቀድሞ 2ኛ በመሆን የብር ሜዳሊያ አግኝቶ ነበር።

በአንድ እሎምፒክ ታሪክም ረጅም ኪሎ ሜትሮችን ሸፍኖ የሮጠ ኢትዮጵያዊ በመሆን በብቸኝነት ስሙ ይጠቀሳል።

ክብርና ሞገስ ለጀግናው አትሌት ሻምበል ማሞ ወልዴ 🙏

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Oct, 20:21


ዐፄ ኃይለሥላሴ ከአለማያ ሐይቅ ከመስመጥ የሞት አደጋ ስለተረፉ የተገጠመላቸው የሙገሳ ግጥም (1916 ዓ.ም)

👇
https://youtube.com/watch?v=YdJludYWmzs&si=5y_0tQcx8eW44tkX

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Oct, 16:05


ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ በምዕራብ ጀርመን ለአራት ቀናት ያደረጉት ይፋዊ የስራ ጉብኝት አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ የተደረገላቸው አቀባበል ፤

አዲስ አበባ ፤ መስከረም -- 1966 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

18 Oct, 15:44


ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም ከባለቤታቸው

ከልዕልት አይዳ ደስታ ጋር ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

16 Oct, 19:04


የበረሃዋ ንግስት ከተማ ድሬዳዋ ፤

የምድር ባቡሩ ጣቢያ እና የመንገደኞች ዕቃ በዘመኑ

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

16 Oct, 18:43


(Google) ጎግል ካምፓኒ ለጀግናው አትሌት ሻምበል አበበ ቢቂላ የ 81ኛው ዓመት የልደት ቀኑን በማስመልከት እንኳን ተወለድክ በማለት በሮም ኦሎምፒክ በባዶ እግሩ ሲወዳደር የመጨረሻውን መስመር ሲያልፍ የነበረውን የምስሉን ገፅታ በፊት (Search Engine) ገፁ ላይ አቅርቦት ነበር።

ነሐሴ 1 ቀን 2005 ዓ.ም

ዘላለማዊ ክብር ለጀግናው አቤ 🙏

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

16 Oct, 17:35


አዲስ አበባ ከተማ በዘመኗ ፤

ህዳር 1967 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Oct, 18:25


አስካለ ነጋ ቦንገር

በ 1966ቱ አብዮት የወጣቶች ንቅናቄ ወቅት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ሳለች ኢትዮጵያ ዜጎቿ በእኩልነት የሚኖሩባት የተሻለች ሀገር ለማድረግ ህልም ቋጥራ መስዋእት የከፈለች የነፃነት ሰማእት ናት።

በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለመጀመርያ ጊዜ በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች በኢሕአፓ ስር ተድራጅተው ከወንድ ጓዶቻቸው ጋር ጎን ለጎን በመቆም የደርግ ፋሺስታዊ አገዛዝን በመቃወም የስርአትን ለውጥ ለማምጣት ታግለዋል ፤ እራሳቸውንም አሳልፈው ለትግሉ ሰጥተዋል።

ከእነኝህ እንቁና ጀግና ወጣቶች አንዷ አስካለ ነጋ ናት። በ 1966 ዓ.ም አስካለ ነጋ በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ በአራት ኪሎ ካምፓስ የሳይንስ ፋኩሊቲ ውስጥ በብዙ ጓደኞቿ "አስኩ" በመባል የምታወቀው አስካለ ነጋ ያኔ 2ተኛ አመትን ጨርሳ ወደ 3ተኛ አመት እየገባች ነበር።

የወ/ሮ አበበች ወ/ጊዮርጊስና የአቶ ነጋ ቦንገር ልጅ የሆነችው አስካለ በጓደኞቿ በጣም የምትወደድ፤ ተግባቢ በጣም ደግና እሩህሩህ እንደነበረች ብዙዎች ይናገራሉ።

በትምህርቷ በጣም ጎበዝ የነበረችው አስካለ የመጀመርያ ደረጃ ትምህርቷን በአፄ ልብነድንግል የ 2ተኛ ደረጃ ትምህርቷን ደግሞ በመድሃኒዓለም ት/ቤት ካጠናቀቀች በኋላ በከፍተኛ ውጤት አልፋ ከቀዳማዊ ኃይለሥላሴ እጅ የወርቅ ቀለበት ተቀብላ ፤ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ገብታ ተከታትላለች።

አስካለ በኢሕአፓነት ስትታገል ቆይታ በ 1970 መጨረሻ አካባቢ በአንጃዎች ጥቆማ ተይዛ ለእስር ስትዳረግ የድርጅቷን ሚስጥር ላለማውጣትና ጓዶቿን ለፋሺስት ደርግ አሳልፋ ላለ መስጠት cyanide...(መርዝ) በመዋጥ እራሷን በማጥፋት በጀግንነት ተሰውታለች። አስካለ የፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ታላቅ እህት ነበረች።

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

15 Oct, 17:37


የዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ሐውልት ታሪክ

ኢጣሊያኖች በመጀመሪያው የአድዋ ጦርነት ላይ በሽንፈት አንገታቸውን ደፍተው እና በውጊያ ተሸንፈው ተባረዋል።

ሆኖም በ 1928 ዓ.ም ለ 2ተኛ ጊዜ ሀገራችን በወረሩበት ጊዜ የመጀመሪያው የሽንፈታቸው ታሪክ እልህ አና ቁጭት ውስጣቸው ስለ ነበረ ሀምሌ 4 ቀን 1928 ዓ.ም በአዲስ አበባ የሚገኘው የዳግማዊ አፄ ምኒሊክ ሀዉልት በምሽት ከቆመበት ስፍራ ነቅለው በምስጢር ቀበሩት።

ከዚያም በጀግኖች አርበኞች የኢትዮጵያ ህዝብ ተጋድሎ ጣሊያን በማሸነፍ ኢትዮጵያ ከፋሺስት ነፃ በሆነችበት ጊዜ ሀውልቱ ከተቀበረበት ወጥቶ በሚያዝያ 27 ቀን 1934 ዓ.ም ዳግመኛ በቦታው እንዲቆም ተደረገ።

ክብር ለኢትዮጵያውያን አርበኞቻችን !!!

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Oct, 19:56


ከ 1952 ዓ.ም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ -ክርስቲያን ፓትርያርክ ሆነው የተሾሙት ስድስቱ ፓትርያርኮች ፤

#ታሪክን_ወደኋላ
#TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Oct, 12:46


ጥቅምት 3 ቀን 1957 ዓ.ም

#በዛሬዋ_ዕለት

ከ 60 ዓመት በፊት ልክ በዛሬዋ ቀን ገጣሚ ፣ ሰዓሊ፣ ቀራፂ ፣ ሙዚቀኛ ፣ ፖለቲከኛ ፣ የፎቶግራፍ ባለሙያ ፣ ነጋዴ ፣ ሹፌር እና ባለቅኔ.....የነበሩት ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በተወለዱ በ 88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩበት ዕለት ነበር፡፡

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

13 Oct, 10:41


https://youtu.be/sMwSO1wcWOA?si=eCZ4M0PK9FrXuLbw

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

11 Oct, 13:09


ግርማዊ ቀዳማዊ አጤ ኃይለሥላሴ ከ 3ቱ ወንድ ልጆቻቸው ጋር

➺ ልዑል ሳህለሥላሴ ኃይለሥላሴ
➺ ልዑል አልጋወራሽ አስፋወሰን ኃይለሥላሴ
➺ ልዑል መኮንን ኃይለሥላሴ

በቀድሞው ነገት ልዑል ቤተመንግሥት የአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፤

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11

ታሪክን ወደኋላ - Tarikn Wedehuala

09 Oct, 17:10


ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ

በድሬደዋ የምድር ባቡር ጣቢያ

በ 1925 ዓ.ም

#ታሪክን_ወደኋላ #TariknWedehuala

youtube.com/@tariknwedehuala11