Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

@ademeteku


Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

18 Oct, 19:13


ታናሽ እህቴ ናት በአስራ ሶስት አመት እበልጣታለሁ ። እሷ ላይ ያለኝ ስልጣን የአለቃ ነው ። 'exercise' የማደረገው ስልጣን ብዙ ነው የአፍሪካ መሪዎች ዜጎቻቸው ላይ ካላቸው ስልጣን አያንስም ። እሷም ስልጣኔ ነው ብዬ 'exercise' የማደርገውን በፀጋ ተቀብላለች ።

ልጄ ትመስለኛለች ምግብ በጋራ ስንበላ ቀድሜ ነው በቃኝ የምለው ። ከሷ ጋር እንዳልሻማ ፍቅሬ እና ሃላፊነቴ ይገታኛል ።

ሁኔታዋን አየዋለሁ ሲዶክካት፣ ስትደሰት እንቅስቃሴዋን አስተውላለሁ ። ከጓደኛዋ እንዳታንሳ 'Invest' አደርግባታለሁ ።

የሆነ ፊልም እያየን መጥፎ ገፀባህሪ ስታይ "ኤፍሬም ፊልም ስለሆነ ነው እንጂ: እንደዚህ አይነት ሰው በትክክለኛ ህይወት የለም አይደል? " ትላለች

ሰው የማርያምን ስም ጠርቶ የሚዋሽ አይመስላትም ፣ ለገንዘብ ብሎ ሰው ጓደኛውን የሚክድ አይመስላትም ፣ የውሸት ለቅሶ ያለ አይመስላትም ። ንፁህነቷ ያስደነግጠኛል ። ብስለት የሚባለውን እውቀት ማጥመቅ ፈልጌ አጠማመቁ ግራ ይገባኛል ።

ስለዓለም ክፋት መንገር እጀምር ና አለምን የምታይበት መነፅር እንዳይንሸዋረር እሰጋለሁ ።

'Feminist ' አደረገችኝ። ትሁቴን እያሰብኩ መደፈር፣ ድብደባ፣ ጭቆና እቃወማለሁ ። ትሁቴን ስለማስብ ሴት አታልሎ ወደ አልጋ መውሰድ አልችልም ። ትሁትን እያሰብኩ ገራገር እንስቶች ላይ 'Advantage ' ለመውሰድ አልሞክርም ።

ትሁቴ የመጀመርያ ልጄ ነች ። በሷ ጉዳይ አልራቀቅም ፣ በሷ ምክንያት ሴቶች ላይ በደል አልሰራም ።

ትሁቴ እንዳትኮርጀኝ ሰክሬ አልንገላወጅም ፣ የማይረባ ጓደኛዬን እቤታችን አላመጣም ፣ ትልቅ ለመሆን እባትላለሁ ።

የአንዳንድ ታናሽ አሻራ እንደ መምህር አይነት ነው !!
© Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

06 Oct, 18:15


የሆነ ቀን አሞኝ አልጋ ላይ ብዙ ጌዜ ከረምኩ ምኔም እምድን አይመስልም ነበር እሚያስቡልኝ አምላክ ሞቴን ቢያፋጥንልኝ ጥሩ እንደሆነ በልባቸው የተመኙልኝ ይመስለኛል ...

እኔ ግን ዳንኩ

የሆነ ግዜ ሱስ ጀመርኩ ጫት ሲጋራ መጠጥ ፊቴን እስኪቀይረው ተከተብኩ አዬ መና ቀረ ተባልኩ

እኔ ግን ሱስ አቆምኩኝ ።

የሆነ ቀን ጓደኞቼ ሁሉ አልፈው እኔ አስረኛ ክፍል ወደኩ ሁሉም በጋራ አዘኑልኝ ብለን ነበረ አሉኝ ሰፈር ቀረ አሉኝ እኔ ግን ተመልሼ private ተፈትኜ አልፌ እስከሁለተኛ ድግሪ ድረስ ተማርኩ

የሆነ ግዜ እናቴ ለቆሶ ልቴድ ፈልጋ ነጠላ ስትበደር አይቻት እኔ ሳድግ አምስት ቅያሪ ነጠላ እገዛልሻለሁ አልኩኝ የሰሙ ሰዎች ሳቁብኝ ለምን እንደሳቁ አላቅም እኔ ግን ስራ ስይዝ አረ አምስት ነጠላ ምን ይሰራል እያሉኝ ጥለቱን እየቀያየርኩ ገዛው ....

ትላንት ብዙ አይሆንምን አልፌያለሁ ። ብዙ አበቃለትን ተሻግርያለሁ ፣ ነገ የተሻለ እንደሚሆን ትላንት ምስክሬ ነው ።

መሞከር ፣መማር፣ ለመሻሻል መጣር ፣መታገስ አናቆምም ሁሉም ይስተካከላል
©Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

27 Sep, 22:39


በጣም ደስስ ያላችሁ መቼ ነው ??

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

25 Sep, 06:25


የምወደው ልጅ ነበር ። እርጋታው ህልሙ መልኩ ሁኔታውን
እወደዋለሁ ስህተቱን ድክመቱን ሳይቀር ነበር የምታገሰው ።

ብጥር ...ብጥር... ከኔ ጋ ማቆየት አልቻልኩም ።

ጊዜ ሄደ ...

እኔም ሄድኩኝ

ሌላ መስመር ሌላ ኑሮ ሌላ ጠዓም አየሁኝ እሱ
ዘግይቶ ወደ ምፈልገው መንገድ መጣ

ዳር ዳር አለ እንዳልገባኝ ሆንኩኝ እብረን እንድንሆን ጠየቀኝ ..ዋጋሽ ገብቶኛል ወድጄሻለሁ አለኝ ።

አልታበይኩም አልጎረርኩም ሰነፍ ነው ቀድሞ ደርሶ ባረፈደ የሚያሾፈው ። ብስለት የሚለካው የሆነልን ሲመስለን በያዝነው አቋም እና ሁኔታ ነው ።

በትህትና አልችልም አልኩት ።

Timing is every thing ፀሎቴ ውስጥ ህልሜ ውስጥ ቅዠቴ ውስጥ ማሳካት የምፈለገው ውስጥ እምይዘው አቋም ውስጥ እሱ ነበር ። ጊዜ ሁኔታ አጋጣሚ ተደራረበ እና አንዱም ውስጥ ጠፋ !!

ምንም ስላላዋጣ ግዜ ልቤ ውስጥ የተወለደውን ፍቅር አደብዝዞት ነበር ። ልቤ ውስጥ የተከማቸውን ፍቅር ስላልወደደው ፍቅሬን ፊት ነስቼው በግዜ ብዛት ተነነ ።

ብቻ መወደድ ከብዶኝ ስለነበር ሳስታውሰው እረፍት አይሰማኝም ነበር ። እረፍት የሌለው ፍቅር ምኑን ፍቅር ነው ??

ናፍቆኝ ጓጉቼ ሳገኘው አይኑ ለኔ ስሜት አልባ እንደሆነ ስለሚነግረኝ ናፍቆቴ ወደ ድብርት ይቀየራል ።

የሚለኝን ያደረገውን የሆነውን ሁኔታውን ትርጉም አየሰጠው ስቀምር የማድር እንደነበርኩ እኔን ካልሆነ አይገባውም !!

ዛሬ ሁኔታሽ አንቺነትሽ ሁሉ ትርጉም ሰጠኝ አብረን እንሁን አለኝ ። ዘግይቶ ነበር Timing is every thing

እንደማይሆን እያወኩ ፍላጎት እንዳለኝ ምልክት ሰጥቼ አልበድለውም !!

" አልችልም" አልኩት

ቁርጣችንን አልነግር እያሉ እንደሚበድሉን መሆን አልፈለኩም ተፈላጊ የመሆኔን እርሃብ ለማስታገስ ወለም ዘለም እያልኩ አልበድለውም

በትህትና " አልችልም ሌላ የህወት መንገድ ላይ ነኝ " አልኩት ። እየመከርኩ አልተመፃደኩም ። መልካሙን ሁሉ እንዲገጥመው ግን በልቤ ተመኝቼለታለሁ ።

ትክክለኛ ነገር ትክክለኛ የሚያደርገው timing ነው !
timing is every thing እንዲሉ አበው!!
© Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

25 Sep, 06:24


እናቴ ስሟ ጌጤ ነው ። ጉሊት ነበር የምትውለው፤ ሻሜታ ትሸጥ ነበር። ትምርት ከሌለኝ ይዛኝ ትሄድ ነበር። አዘንጣኝ ነበር የምትሄደው እኔ ከሌለሁ ልጄን ይመቱብኛል ብላ ነበር መስርያ ቤቷ የምትወስደኝ ።

መስርያቤቷ አጥር ፣ ጣርያ፣ የለውም። ወለሉን ድንጋይ ረብርባ ከፍ አድርጋዋለች።
ጥግ ላይ የምትቀመጥበት ወደጎን የረዘመ ዱካ ነበራት።

ደግ ናት፤ ፀሃይ ቀጥቅጧት የምታመጣውን ገንዘብ አትሰስትም ። ስትሰራ ውላ ደከመኝ እያለች ስትማረር ሰምቻት አላውቅም።

በየምክንያቱ "ቸርነቴ" እያለች ትጠራኛለች ።

አንገቷ ረጅም ነው ሃብል የሚመስል ንቅሳት አንገቷን አጥለቅልቆታል ። ከፊቷ ፈገግታ አይጠፋም ። ለለማኝ ገንዘብ ሰጥታ ሲመርቋት ሁለት እጇን ዘርግታ "አሜን አሜን" ትላለች። ጥሩ ነገር ከተደረገላት "ግንባርህ አይታጠፍ ...እግዚአብሔር ይስጥህ.....
አትጣ ...ጤና ይስጥህ" ትላለች።

ሰው ትወዳለች ፣ ስራ ትወዳለች ፣ አመስጋኝ ናት ...
የዚች ልጅ ተሁኖ ሰነፍ እና ክፉ መሆን እንዴት ይቻላል ? !
© Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

20 Sep, 20:12


የአንድ አባት ምክር ፦

ሃብታም ነው ብለህ ፣ስልጣን አለው ብለህ ፣ ያሳልፍልኛል ብለህ ፣ ያግዘኛል ብለህ፣ ባለሃብት ነው ብለህ ቀልቡን ለመግዛት የምትሆነውን መሆን በፊቱ ሞገስ ለማግኘት ብለህ የምትሄደውን እርቀት

ለአምላክ ብታደርገው

ታሪክህ ይቀየራል !!
©Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

19 Sep, 20:22


ተሰብሬ አውቃለሁ ሁኔታዬ አይመስልም አይደል ?? ጀርባዬን ሰጥቼ ቆሜ ተገፍቼ አውቃለሁ አወዳደቄን ያከፋው የገፋኝ ሰው ላይ የነበረኝ እምነት ነው !!

እምነቴ ሲናድ ድባቴ መላአካላቴ ውስጥ ተሰራጭቶ ነበር ። ጠዋትም ማታም ስተኛ እና ስነሳ የሚሸኘኝ ድባቴ ነበር ።

ቀን ተጠራቅሞ ድባቴ ሞተ !!

የጣለኝ አይነት ተግባር ሳይ ድባቴዬ ከሞተበት አፈር ልሶ ይነሳል ።

ማን ነበር የሰበረኝ ???

እኛ ማለት ያላወራነው ገመናችን ነን !!

ገመናችን ፍርሃታችን ውስጥ ፣ ብዙ የማናብራራው ሃሳብ ውስጥ፣ አልያ ከምናወራው በተቃራኒ የቆመ ሃቅ ውስጥ ጥቅልል ብለን የተደበቅን ይመስለኛል

ስለ እምነት የሚተነትነው የተካደ ወይ የካደ ይመስለኛል ፣ ስለሃብት የሚተነትነው ገንዘብ ገዢ እንደሆነ በሆነ መንገድ ጀርባውን የገረፈው እውነት ያለው ይመስለኛል ?

ዋጋ ያላስከፈለን ነገር ቢኖረንም በየደቂቃው አናስታውሰውም!!

ሃይለኛ ነኝ ፣ ሃይለኛ ነኝ ፣ ሃይለኛ ነኝ የሚለው ሰነፍ ነው ደካማ ነው ብለው እንዳያጠቁት የሚፈራ የመስለኛል .... :-

እኛ ያላወራነው ወይ ብዙ ግዜ የምናወራው ተቃራኒ ነን እላለሁ ...!

ሰው አዘውትሮ ከሚተነትነው ጉዳይ ጋር ያስተሳሰረው የህይወት ድር አይጠፋውም ሳይፈልገው ምላሱ አይኑ ጆሮው ቀልቡን ይስብበታል ።

ማን ነበር ግን የሰበረኝ ??

የተሰበርንበት ቦታ ፣ ታሪክ ፣ ሁኔታ ፣ አይነት ይለያያል እንጂ ማን አለ ያልተሰበረ?!
©Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

07 Sep, 18:25



ከውድቀታችሁ ጋር ለማያብሩ ፣አሳልፈው ለማይሰጧችሁ ፣ በሌላችሁበት ለሚከራከሩላችሁ ፣ ስትደክሙ ሊያጠነክሯቹ ለሚታትሩት

ችርስ ለነርሱ 🙏

ጥሩ ነገር ሲያገኙ ለሚያጋሯችሁ ፣ ስታጠፉ ለማይስቁላችሁ፣ ለሚፀልዩላችሁ፣  የማትወዱትን ነገር ሆነ ብለው ለማያስታውሷችሁ፣ መውደዳቸው ምላሳቸው ላይ ብቻ ለሌለ ቅን ሰዎች

ችርስ ለነርሱ  🍷🍷
ኑሩልን

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

06 Sep, 12:13


"ትንሽ ቦታ"

ስሜታዊ ሆኖ ለተናገረን ፣ ሊረዳን ፈልጎ ለሳተ ፣ ኑሮ አስክሮት ለገፋን ፣ ንዴት ገፍቶት ላጠፋ ፣ ግዜ አጣሁ ብሎ ላልጎበኘን ፣ ስናሸንፍ ላላጨበጨበ፣ ስንወድቅ ላላነሳን ፣ ስናስብለት ላልተረዳን ፣ ማደጋችንን ላላየ ፦

"ትንሽ ቦታ ለይቅርታ" አኑረናል

አማረልን ብለን ላሳዘንን ፣ አጉል ተስፋ ለሰጠነው ፣ ውድቀት ላይ ለሳቅነው ፣ ብልግናን ላጎላናው ፣ ድድብናን ላነፈስነው ፣ ማድረግ ችለን ላላደረግነው ፣ ችለን ለተጣመምነው ።

ለራሳችን ይቅርታ አደርገናል...

ቺርስ ለአዲስ ዘመን
ቺርስ ለተስፋችን
ቺርስ🙏.
©Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

05 Sep, 20:31


ኤደን ደማቅ ጥቁር ነች ። የጥርሷ እና የአይኗ ንጣት ጥቁረቷን ያጎለዋል ። ልበ ደንዳና የምትባል አይነት ነች ። አወራሯ ፣ አደናነቋ ፣ አገራረሞ የእናት ነው።

ተንከባካቢ ነች ።አባቷ ስድስት ኪሎ university ያስተምራል ፤ ምስጉን የታሪክ ፕሮፌሰር ነው ።

መጀመርያ አካባቢ ሁኔታዬን እያየች የግርምት ፈገግታ የፈገገች ይመስለኝ ነበር ( አሁን ፈርዶብኝ እንጂ ፈገግታን መመርመር ነበረብኝ? )

ኤደንን አወቅኳት ፤ ሳውቃት አመንኳት ፤ እሷ ጋ ነፃ ሆንኩ ። ድሮ እናቴ ጋ ስሆን የሚሰማኝ 'security' ይሰማኛል።

ኤዱ ጥያቄ መጠየቅ ትወዳለች ።

ስለራሴ ተጠይቄ የማላውቀውን ፣ አስቤው የማላውቀውን ፣ ደጋግሜ ያሰብኩትን ነገር በፍቅር ትጠይቀኛለች

ለራሴ እንደማወራ ሆኜ ሳልጠነቀቅ ፣ ሳልሰጋ አጫውታታለሁ ። ትሰማኛለች አሰማሟ ርህራዬ አለው ። ሳወራ በትኩረት እንደ ተከታታይ ፊልም አይኗን ፣ ጆሮዋን ሰጥታ ትከታተለኛለች ።

ከራሴ ጋ እተዋወቅ ጀመር ። ገጠመኝ ያልኩትን 'incident' ጠቅላላ ስቶሪ አደረገችልኝ ። ሳወራት ቀለል ይለኛል ።

"መንገደኛው ሁሉ ይወቅኝ አልልም ። ልቤ ውስጥ ያለውን እውነት በእኔ ልክ ሁሉም ጋ ይስረፅ አልልም ። እንከን አልባ ለመሆን አልሞክርም"ያለቺኝ ቀን ያለቺው እውነት እንደነበር ኑሮዋን ሳጤነው ደረስኩበት

ታድላ አልኩ !

ሁኔታዋ ከሰዎች ጋ ያላት መቀራረብ ሰላማዊ ነው ። ራሷን በየቦታው አታስረዳም ። ስለ'ኔ ሳወራ እኔም እኔም እያለች እንደ'ኔ ጨዋታ አታደፈርስም ።

የሆነ ሰው ቱግ ሲል ፣ በተገቢው "treat" ካላደረጋት በእርጋታ ታስረዳለች ፤ አልያ ታልፈዋለች አባቴ "ሰነፍ ነው ለአፀፋ የሚቸኩለው ይላል" ትላለች ።

የሆነ ቀን እያወራን
"ከሁሉም ነገር ጋ ራስን ማገናኘት ፤ በሁሉም ቦታ ራስን ለማስከበር መሞከር ፤ ሁሉም ሰው ቀልቡን ይስጠኝ አይባልም" አለችኝ። አባባሏ እንደምክር አይደለም ቀለል አድርጋ ነው። በጊዜው ያስፈልገኝ ነበር ፤ የወረወረቺው ሃሳብ ሳልከራከር ፣ ሳላብራራ ዋጥኩት

ራሴን በእርጋታ እንዳጤነው ፍርሃት እና ስጋቴን እንዳየው አደረገችኝ ።

ትላፋኛለች ፣ ትስመኛለች ፣ ታደምጠኛለች ። ቅሬታዬን ስነግራት "ትክክል ነው ግን እስቲ እንደዚህስ ሊሆን አይችልም?" ትላለች ።

ከብዙ አቅጣጫ ሁኔታውን ታሳየኛለች ። ስናደድ ፣ ሲደብረኝ በጥሞና ሁኔታዬን ማኔጅ ማድረግ አለመደችኝ ።

ቅር ያለኝን ነገር ተረጋግቼ እንድናገር ፤ ምንም አይነት ኮተት ሃሳብ አልጋ ላይ ይዤ እንዳልሄድ ሁሉንም ነገር በ "serious" እንዳልወስደው በኑሮዋ አስተማረችኝ

Don Miguel Ruiz የፃፈውን The Four Agreements"
Mark Manson የፃፈውን The Subtle Art of Not Giving a F*ck" Eric Ries የፃፈውን "The Lean Startup"
የአቡነ ሺኖዳን የነፍስ አርነት Daniel Goleman የፃፈውን "Emotional Intelligence" ብዙ መፅሃፎችን በቁምነገር እየተከታተለች አስነቡችኝ

እሷ ኑሮዋ ፣ ፍቅሯ ያስነበበችኝ መፅሃፎች

አዳኑኝ !

ጎበዝ አስተማሪ ነበረች ፣ ጎበዝ ተማሪ ነበርኩ እና
ዳንኩ !
መፈለግ እና መትጋት የማያበጀው ነገር የለም !!

© Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

05 Sep, 20:25


በጨረፍታ የተሰማ ፀሎት

አምላኬ ሆይ፦ ፀሃይ ከመንገድ ወጥቼ
ይቀጥቅጠኝ ፤ዶፍ ዝናብ መጠለያ አጥቼ ይደብድበኝ ፤ የታክሲ ሰልፍ ያማረኝ ፤ የቀጠርኳት እንስት ቀርታብኝ ሰፈሯ ሄጄ ልንጎራደድ ይሄ ሁሉ እንዲሆንብኝ ከዚ አልጋ ብቻ አላቀኝ እንደሰው ልራመድ 🙏
.
.
የብዙ ሰው ምሬት ላንዳንዱ የሰርክ ፀሎቱ ነው።

©Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

21 Aug, 22:32


Life is a beautiful lie💔

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

21 Aug, 22:32


ተሳካላት አሉኝ እየተሳቀቁ እማዝን መስሏቸው ..

.....ስስቅ ገረማቸው

ተያቸው !!

ስኬትሽ .....

አብረን የወጠነው ፣አብረን ያወጣነው፣ አብረን ያወረድነው ፤ ፀሎቴም መሆኑ ስላልገባቸው ነው !!!
@adhanom mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

21 Aug, 08:46


ድሮ... ቆንጆ ስለሆነች ብቻ ነበር የወደድኳት ። ስቀርባት አራዳ ናት! አንድ ቀን በፀሃይ ተገናኝተን ስንቃደድ፥ ስንጫወት አስተናጋጇ መጥታ ይቅርታ ልወጣ ነው ሂሳብ አለችን ...

ፈረቃዋን ጨርሳ ልትሄድ መስሎን ነበር፤ ለካ መሽቶ ሊዘጋ ነው። የምንወደው ሰው እንደኛው መለክያ ስናገኘው ሰዓቱ አልመጎተቱ ነው አይደል?

ያልተመቸን ቦታ ሁሉ ሰዓቱ አይበርም!!
ተፈጥሮ እንደ ምላስ We had an amazing time!! ብሎ አይዋሽም!!

ስቀርባት መልኳን ትበልጠዋለች ...!

ከሚሰማት 'ርቃ አታስመስልም፤ ጥላቻ አያሳድዳትም ፣ የበታቾቿ ላይ አትቀማጠልም። የወደቀ ላይ አትንጠራራም... ደስታዋ ቁስ ላይ አልተንጠለጠለም...።

ትወጂኛለሽ እላታለሁ...?

አስከሰማይ ነው የምወድህ ትላለች...አንገቴ ስር እየተወሸቀች። አወዳደዷ ስር አለው...ድንገት ተገንብሮ ውድቅ ሊል ይችላል የሚባል አይነት አይደለም።

እዚህ ጋ...መዋደድ ባይኖር መኖር ይሰለቻል ብለን መኖርን እናበሽቀዋለን!!
© Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

21 Aug, 07:37


ከእንቅልፌ ስነቃ ደሞ ነጋ ብዬ አውቃለሁ ። አስር ብር ወድቆብኝ የማንሳት አቅም አጥቼ ከዛፍ እንደወደቀች ቅጠል ቸል ብያት አውቃለሁ ።

አይኔን እያዩ ሲያሳንሱኝ ሳይደብረኝም ደስ ሳይለኝም ቀርቶ ያውቃል ..... እየተሰደቡ ስሜት አልባ ፊት ማሳየት እንዴት ተቻለኝ... አልኩኝ

የሆነ ቀነ እንደዋዛ ኑሮዬ ላይ ገባች .... አለባበሷን በደንብ ስመለከት ውበቷ ሲታየኝ ባወራችው ጎረምሳ ስቀና እሷን ለማግኘት ቶሎ ቶሎ የሚያድገውን ፂሜን ስቆረጥ ለሁለት ብር ከረዳት ጋ ስጨቃጨቅ ...

ያላመነቺኝ ሲመስለኝ ስምል ...አልገባኝም ደግመሽ አብራሪልኝ ስላት

"ዛሬም አታገኘኝም እንዴ ?" ስትለኝ ቀጠሮ ስሰርዝ ...ፖለቲካው ኢኮኖሚው ተጭኖኝ ችላ ስለው
.
.
ለደበረው ሰው አዚ ጋ አንድ ፍቅር አምጣለት ማለት ስከጅል

ምን አልኩ መሰለሽ .....
'ባልወድሽ ኖሮ ድብርትን አልችለውም ነበር '
©Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

18 Aug, 19:38


እናቴ ሁሌ ነበር አግቢ የምትለኝ ፣ በተረት ፣በታሪክ በሃዘን አስታካ ስለ ትዳር ነበር የምትወተውተኝ ። በመወትወት ከማይሆነው ነገር ውስጥ አንደኛው ትዳር ነው ።

ውትወታዋ በቶሎ ፍሬ አላፈራም ። ውትወታዋ ስለሚያስጨንቀኝ ክፍት ያለ ፊት ሳሳያት ጨዋታ ትቀይራለች ።

አብሪያት ሳድር ፀሎቷ ውስጥ በየቦታው አለሁ ።

ሰመረልኝ እና ....!

" እናቴ ላገባ ነው የምወደዉ ልጅ አግኝቻለሁ መስመር እስኪይዝ ነው ያላጫወትኩሽ"

"ምን አልሺኝ ?"ብላ ብድግ አለች

እጮኛዬ ሽማግሌ ሊልክ ነው አልኳት።

እምባዋ ቃላቷን ቀደመው !

ጥሩ ሰው ነው ?? ትዋደዳላቹ ??

"አዎ" አልኳት በፈገግታ ሌላ አልጠየቀችኝም ።

አገላብጣ ሳመቺኝ ። ደስታዋ ወደር አልነበረውም ።
አንጋጣ ተመስገን አለች ።

ደስታዋ አንጀቴን በላኝ ። እናት ከሃዘናችን በላይ ደስታችን ያስለቅሳታል ። የልጅ ሃዘን ለእናት እምባ አይደለም ስብራት ነው !!

መሰበር የምንፈራው ለሚወዱን ሰዎች ብለንም ነው ። እኛ እኮ የኛ ብቻ አይደለንም !!
© Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

17 Aug, 04:30


ሙስሊም ነው ። ለአላህ የሚታመን ሙስሊም ።

ለአላህ የሚገዛ'ው አላህ የማይወደውን ባላማድግ ነው ። አላህ የማይወደው ተደረገ ብሎ በስድብ ዘብ ሲቆም፣ ሲጣላ አይቼው አላውቅም ።

ሱሪው ያሳጥራል ፣ፂሙ እጅብ ያለ ነው ። ፈገግታው ፈራጅ እንዳልሆነ ምስክር ነው ። ሃጥያቴን ስነግረው አንዱን እንኳን ሳልቀንስ ነው ፣ እያዘነ ነው የሚሰማኝ ፣ "አይዞሽ ዱኣ አደርግልሻለሁ ወላሂ !! " ይላል

እረጋ አባባሉን እወደዋለሁ !! ሲራመድ አረማመዱ ጥድፊያ የለውም ። እሚያቀውን ሲናገር መታበይ የለበትም።

ፊቱ ላይ ፈገግታ አይጠፋም ።

ደስ ይላል ። ማንም ፊት የማላደርገውን እሱ ፊት አደርጋለሁ ለማንም የማልነገረውን ለሱ እነግራለሁ።

ለአላህ ታማኝ ነው !

ምግባሩ ፣መንገዱ ፣ ወሬው ምስክር ነው !!
ለኣምላኩ ታማኝ እንደሚሆን ቅዱስ የለም ፣ ደብቆ እንደሚሰጥ ቅዱስ የለም ፣ የሰው ሃጥያት እያዘነ አንደሚሰማ ቅዱስ የለም ።

ሳገኘው እረፍት ይሰማኛል !!

ያልጠበቀውን ትንሽ መልካም ነገር ሳደርግለት ፊቱ ላይ ደስታ ይጥለቀለቃል ። አይኑ እምባ ሙልት ይላል በደስታ ወላሂ አመሰግናለሁ ይላል

ወዳጅነት ያውቃል ፣ ጨዋታ ይችላል ፣ ሰው ነው !!

ወላሂ እወድሃለሁ እለዋለሁ !!
©Adhanom Mitiku

Adhanom Mitiku / አድኃኖም ምትኩ

11 Aug, 10:29


ስለማልችል ነው ....

ክብሬን እየተነካ መሳቅ ፤ መቀራረብን ለማሳየት ለበጣ እና ስድብ አልታገስም ።

የሆነ የስራ እድል አለ ብዬ ፣ የሆነ ጥቅም ስለሚገኝ የሆነ ትልቅ ደረጃ ያለ ሰው ስለሆነ ብዬ በማልወደው መንገድ ሲያወራኝ ደስ እንዳለኝ መሆን አልችልም ።

የሆነ ሰው ደስ እንዲለው ብዬ የማላምንበት ጉዳይ እንዳመንኩ ሆኜ ስተውን መዋል አልችልም ፤ ፋራ ላለመባል አራዳ ለመምሰል ያውቃል እንድባል በሰው የጣዕም ልኬት ስንሸራሸር መዋል አልችልም !!

በነገ ተስፋ መቁረጥ ፣ለማደግ አለመጣር የተሻለ አለመመኘት ፣ለመማር ዝግጁ አለመሆን አልችለም!!

ባለኝ አለመደሰት አመስጋኝ አለመሆን ፤እሚወዱኝን ጨዋ ሰዎች አለመውደድ አልችልም !!

ራሱን ከማያከብር ጋ እይታዬን ከማያከብር ጋ መወዳጀት አልችልም !!

አንዳንድ አለመቻሎች ደስስስ ይላሉ

© Adhanom Mitiku