C R R S A - የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

@addisvaitalpress


C R R S A is a government organization established by law to deliver Civil Registration & Residency services in Addis Ababa. The agency is responsible for registration of vital events & issuance of residency identification within the domain of the city.

C R R S A - የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

23 Oct, 09:07


ማስታወቂያ

በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት ለመመዝገባ ጥያቄ ላቀረባችሁ አመልካቾች

በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት ለመመዝገብ የክ/ሃገር መሸኛ አስገብታችሁ በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተገልጋዮች ያቀረባችሁትን መረጃ የማጥራት ሂደት በማጠናቀቅ አገልግሎቱን ከህዳር 1 ጀምሮ ለመጀመር ዝግጅት ተደርጓል።

በመሆኑም ከነገ ጥቅምት 14/2017ዓ.ም ጀምሮ በነዋሪነት ለመመዝገብ ያመለከታችሁበት የሲቪል ምዘገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት የወረዳ ጽ/ቤታችን እስከ ጥቅምት 22 ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እያሳሰብን የፋይዳ ምዝገባ አስገዳጅና ምዝገባው በኤጀንሲው ጽ/ቤት እዛው የሚከናወን በመሆኑ የክ/ሃገር መልቀቅያ ባስገባችሁበት ወቅት ከጽ/ቤታችን የተሰጣችሁን ማስረጃ ይዛችሁ እንድትቀርቡ በአክብሮት እንገልፃለን።

ውድ ተገልጋዮቻችን በዚህ የማጥራት ሂደት ያላለፈ አመልካች በነዋሪነት ተመዝግቦ አገልግሎት ማግኘት የማይችል መሆኑን በመገንዘብ በተቀመጠው የግዜ ገደብ ዘውትር ከሰኞ እስከ እሁድ ቀርባችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ እናሳውቃለን።

ኤጀንሲው
CRRSA

ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ የስልክ መስመራችን 7533 ደውለው ያግኙን

ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et

ዩትዩብ (youtube)፡ https://www.youtube.com/@CRRSA1935
ፌስቡክ (facebook):

https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686

ቴሌግራም (telegram): https://t.me/addisvaitalpress

ፖስታ ሳ.ቁ (Box No)፡ 20320

C R R S A - የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

22 Oct, 13:59


የቴክኖሎጂ ባለሙያ እና ዓለም አቀፍ አማካሪ አቶ ሰሎሞን ካሳ የኤጀንሲውን ዋና መስርያ ቤት ጎበኙ

CRRSA: ጥቅምት 12/2017ዓ.ም
አዲስ አበባ

እውቁ የቴክኖሎጂ አማካሪ፣ ሙያተኛ እና የEbs የቴክኖሌጂ ፕሮግራም አዘጋጅ አቶ ሰለሞን ካሳ ዛሬ በኤጀንሲው ዋና መስርያ ቤት ተገኝተው ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን ተቋሙ በዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ዘርፍ እያደረገ ያለውን ሪፎርም ተመልክተዋል።

የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ እንግዳውን ተቀብለው ያነጋገሩ ሲሆን አቶ ሰለሞን በበኩላቸው የተቋሙ የመሰረተ ልማት ዘርፍ የተደራጀና በቀጣይ ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ ያለው የሶፍትዌር ልማት ሲጠናቀቅ ከተማውን ስማርት ለማድረግ በሚሰራው ስራ ላይ ያልው ሚና በእጅጉ የላቀ እንደሆነ አንስተው ዘርፉ በከተማው የተሰጠው ትኩረት የሚያስመሰግንና በሙያቸው ለማገዝ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ የስልክ መስመራችን 7533 ደውለው ያግኙን

ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et

ዩትዩብ (youtube)፡ https://www.youtube.com/@CRRSA1935
ፌስቡክ (facebook):

https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686

ቴሌግራም (telegram): https://t.me/addisvaitalpress

ፖስታ ሳ.ቁ (Box No)፡ 20320

C R R S A - የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

22 Oct, 12:19


ኤጀንሲው 70 የወረዳ ጽ/ቤቶቹን የነዋሪ መረጃ ማደራጀ ማህደር ክፍል ለማዘመን ከጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር የፕሮጀክት ስምምነት ተፈራረመ

CRRSA: ጥቅምት 12/2017ዓ.ም
አዲስ አበባ

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ በተቋም ሪፎርም መርሃ ግብሩ የነዋሪውን መረጃ በዘመናዊ መልክ ማደራጀት መሆኑ ይታወቃል።

በዚሁ መሰረት በሁሉም ክ/ከተማ ያሉ 70 የወረዳ ጽ/ቤቶችን የማህደር ክፍል በዘመናዊ እና ወጥ በሆነ ሁኔታ ለማደራጀት የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ በተገኙበት ከጄኔራል ዊንጌት ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር ስምምነት ተፈፅሟል።

ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ የስልክ መስመራችን 7533 ደውለው ያግኙን

ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et

ዩትዩብ (youtube)፡ https://www.youtube.com/@CRRSA1935
ፌስቡክ (facebook):

https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686

ቴሌግራም (telegram): https://t.me/addisvaitalpress

ፖስታ ሳ.ቁ (Box No)፡ 20320

C R R S A - የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

21 Oct, 08:24


C R R S A: ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም


በሀሰተኛ መታወቂያ የጋብቻ ሰርትፍኬት እና የልጃቸው ልደት ለማግኘት የሞከሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ


በየካ ወረዳ 7 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ፅ/ቤት በቀን 9/2/2017 ዓ.ም በሀሰተኛ መታወቂያ የጋብቻ ሰርትፍኬት እና የልጃቸው ልደት ለማግኘት የሞከሩ ግለሰቦች በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጎ ምርመራ እየተደረገባቸው እንደሚገኝ የኤጀንሲው ፀረ- ሙስና ዳይሬክቶሬት አስታውቋል፡፡



ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ የስልክ መስመራችን 7533 ደውለው ያግኙን


ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et


ዩትዩቭ (youtube)፡ https://www.youtube.com/@CRRSA1935


የፌስቡክ (facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686


ቴሌግራም (telegram): httpst.me/addisvaitalpress

C R R S A - የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

18 Oct, 08:09


C R R S A: ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም


በሃሰተኛ መሸኛ አገልግሎት ለማግኘት የሞከረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ


በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11 የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ፅ/ቤት በቀን 29/1/2017 ዓ.ምበሃሰተኛ መሸኛ አገልግሎት ለማግኘት ሙከራ ሲያደርግ የተገኘ ግለሰብ በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገበት እንደሚገኝ የኤጀንሲው ፀረ- ሙስና ዳይሬክቶሬት አስታውቋል፡፡



ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ የስልክ መስመራችን 7533 ደውለው ያግኙን


ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et


ዩትዩቭ (youtube)፡ https://www.youtube.com/@CRRSA1935


የፌስቡክ (facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686


ቴሌግራም (telegram): https://t.me/addisvaitalpress

C R R S A - የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ

17 Oct, 12:25


C R R S A: ጥቅምት 7/2017 ዓ.ም

አዲስ አበባ


ኤጀንሲው ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል ስምምነት ፈፀመ


የሲቪል ምዘገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የሚሰጣቸውን የኩነት እና የነዋሪነት አገልግሎት አፈፃፀም ለማሳደግ የባለድርሻ አካላት ሚና ወሳኝ በመሆኑ በ2017 በጀት ዓመት በጋራ በሚሰሩ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርጎ የስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል፡፡


ከባለድርሻ አካላት ጋር የተቀናጀት የመረጃ ልውውጥ በማድረግ በተለይም ልደትና ሞት 100% ለመመዝገብ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡


የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ ስምምነቱ ከቴክኖሎጂ እና ከአሰራር ስርዓት አንፃር የተዘጋጀ መሆኑን በመጠቆም ከተቋማት ጋር በቅንጅት በመስራት የተሻለ አፈፃፀም ለማምጣት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ስምምነቱ በጋራ ተቀናጅቶ መስራትን መሰረት ያደረገ ሲሆን የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ከሚመለከታቸው የፌደራል እና የአዲስ አበባ ከተማ ተቋማት ተፈራርመዋል፡፡



ለበለጠ መረጃ፣ ጥቆማ ወይም ማብራርያ በተገልጋይ የስልክ መስመራችን 7533 ደውለው ያግኙን


ዌብ ሳይት (website): https://www.aacrrsa.gov.et


ዩትዩቭ (youtube)፡ https://www.youtube.com/@CRRSA1935


የፌስቡክ (facebook): https://www.facebook.com/profile.php?id=100064083391686


ቴሌግራም (telegram): https://t.me/addisvaitalpress