Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

@wanawmedia


Media - ሚዲያ

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

23 Oct, 04:31


በነቀምት ከተማ በተከራየበት ቤት ተሸሽጎ በመቀመጥ ታግቻለሁኝ በማለት  ከቤተሰቦቹ 1 ሚሊዮን ብር የጠየቀው  መምህር በቁጥጥር  ሥር ዋለ

በነቀምት ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ በተከራየበት ቤት ውስጥ ተደብቆ በመቀመጥ በአጋች ሃይሎች ታግቻለሁኝ በማለት ከቤተሰቦቹ በርካታ ገንዘብ የጠየቀው መምህር በቁጥጥር  ስር መዋሉ ተገልጿል ።

የነቀምት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ መረጃ እንደሚያመላክተው  ተጠርጣሪ  ሰለሞን በንቴ የተባለው  የነቀምት ጤና ሳይንስ ኮሌጅ መምህር  የሆነው ግለሰብ ከጎደኛው ጋር በመነጋገር በተከራየው ቤት ውስጥ ተደብቆ በአጋች ሃይሎች  እንደተያዘ በማስመሰል ለማጭበርበር   መሞከሩ  ተገልጿል ።

ግለሰቡ በጎደኛው ለቤተሰቦቹ በማስደወል 1 ሚሊዮን ብር  እንዲልኩ  መጠየቁ ተረጋግጧል ። ተጠርጣሪው  ወደ ባለቤቱ ስልክ በማስደወል  መታገቱን  በመግለጽ እንዲሁም በተጨማሪ  የባለቤቱ  እህት የሆነችው እና ምዕራብ ወለጋ ዞን ጊምቢ ወረዳ የምትኖረዋን ግለሰብ በማስደወል  በሶስት ቀናት ውስጥ 1 ሚሊዮን ብር እንድትልክ በተደጋጋሚ እየደወሉ  ሲያስጨንቋት እንደነበረም ተገልጿል።

የተጠርጣሪው  ቤተሰቦች ገንዘቡን  መክፈል ባለመቻላቸው ጉዳዩን ለፖሊስ  በማስታወቅ ፖሊስ ባደረገው ክትትል ተጠርጣሪው ከነተባባሪው በቁጥጥር  ስር ሊውል ችሏል።

ፖሊስ ጉዳዩን እያጣራ መሆኑንም ገልፆል።

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

22 Oct, 07:59


ያልጨመረ ነገረ ምንድነው??😳

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በይፋዊ ገፁ እንደገለፀው የአገልግሎት ክፍያ ላይ ጭማሪ አድርጓል።

🖊 ለሀገር አቀፍና ለክልላዊ ፖለቲካ ፓርቲ ጊዜያዊ ሰርተፊኬት ለማግኘት 100 ብር ይከፈል የነበረው አሁን 15,000 ብር (አስራ አምስት ሺህ ብር)

🖊 ለሙሉ ዕውቅና ለሀገር አቀፍና ክልላዊ ፓርቲ 200 ብር የነበረው ክፍያ አሁን 30,000 ብር (ሰላሳ ሺህ ብር)

🖊 የተመዘገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች መሰረታዊ ሰነዶቻቸውን በጉባኤ አሻሽለው ሲያቀርቡ 30 ብር ይከፍሉ የነበሩ በተሻሻለው 5,000 ብር (አምስት ሺህ ብር) ገብቷል።
ቤተሰብ በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ 👇
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

20 Oct, 13:21


አዲስ አበባ

"ድንግልና ለባል እንጅ ለእጮኛ አይሰጥም" 😳

https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

20 Oct, 06:30


አዲስ አበባ የተፈፀመ

ትናንት ሜክሲኮ ጋር አንዲት እናት ልጇን ይዛ እየለመነች እያለ ደንብ አስከባሪዎች መጥተው ሂጂ ከዚህ ሲሏት እናትም ይሄው ውሰዱት ብላ ልጇን ጥላ መጥፋቷን ሰምተናል።ያሳዝናል።ኧረ በልክ አድርጉት
https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

19 Oct, 20:54


አዲሱ የመንግስት ስራተኞች ደመወዝ ከጥቅምት ወር ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ የገለፀው የገንዘብ ሚኒስትር ለዚህም የአፈፃፀም መመሪያ መዘጋጀቱን አስታወቀ!

የገንዘብ ሚኒስትር እንደገለፀው የጥቅምት ወር የደመወዝ ክፍያ በአዲሱ በተሻሻለው የደመወዝ ስኬል መሰረት መሆን ይጀምራል ብሏል። ለዚህም በቂ ዝግጅት ከመደረጉ በላይ የአፈፃፀም መመሪያ መዘጋጀቱን አስታዉቋል።

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

19 Oct, 15:42


ወሎ ዩኒቨርሲቲ በድኅረ እና በቅድመ ምረቃ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን 2,224 ተማሪዎች በኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስትቲዩት ግቢ ዛሬ አስመርቋል።

ተመራቂዎቹ በመደበኛ፣ በክረምት፣ በርቀት እና በተከታታይ መርሐግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

በዋናው ደሴ ግቢ 1,980 ተማሪዎች፣ በኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስትቲዩት 199 ተማሪዎች እና በልዕለ ህክምና ግቢ 45 ተማሪዎች በድምሩ 2,224 ተማሪዎች መመረቃቸው ተገልጿል።

በማዕረግ ለተመረቁ ተማሪዎች ልዩ ሽልማት የተበረከተ ሲሆን፤ ከአጠቃላይ ተመራቂ ተማሪዎች ተማሪ አብዮት አሸብር ከኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ የዋንጫ ተሸላሚ ሆኗል።

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

17 Oct, 13:06


አንዲት ላም 3 ጥጆችን ወለደች

📌 በስልጤ ሽማግሌ ትንቢት መሠረት ቀጣይ ብሩህ ጊዜ እንደሆነ ተተንብየዋል።

በስልጤ ዞን አሊቾ ውሪሮ ወረዳ ሽልማት ቀበሌ ላይ ቀጨሞ ልማት ቡድን  አንዲት የሀበሻ ላም ሶስት ጥጆችን ወለደች።

ማክሰኞ ጥቅምት 05/2017 ዓ ም ከቀኑ ሰባት ሰዓት ገደማ የወይዘሮ ሙርሺዳ ሽፋ የሀበሻ ላም ሶስት ጥጆችን በሰላም በመውለዷ ለአከባቢው ማህበረሰብ አግራሞትን ፈጥሮዋል።

ከዚህ ቀደም ይህቺው ላም በአንድ ወሊድ ጊዜ ሁለት ጥጃ መውለዷን ያስታወሱት ወ/ሮ ሙርሺዳ ሽፋ ሶስት ጥጃዎች  መወለድ በእለቱ ድንጋጤ እንደፈጠረባቸው ሳይሸሽጉ ለአሊቾ ኮሚኒኬሽን ገልጸዋል።

ወንዱ ጥጃ ከተወለደ ጥቂት ሰአታት በኋላ የሞተ ሲሆን ሁለቱ ሴት ጥጆች በህይወት አሉ።

አቶ ሀይረዲን አለማር የአከባቢው  ነዋሪና ታዋቂ ሽማግሌ ሲሆን ሁለት ጥጃ  በአንዴ መወለድ አልፎ አልፎ ክስተት መሆኑን አንስተው ሶስት ጥጃ መወለድ በስልጤ ሽማግሌ ትንቢት መሠረት ቀጣይ ብሩህ ጊዜ እንደሚመጣ ተንብየዋል።

በአልቾ ውሪሮ ወረዳ እንስሳትና ዓሳ ፅ/ቤት ባለሙያና አስተባባሪ ዶ/ር መሀመድ ከድር ክስተቱን በማስመልከት በሰጡት ሀሳብ እንደገለጹት በወረዳችን ከዚህ በፊት ያልተለመደ መሆኑን  ገልጸዋል።

በወቅቱ ላሚቷ የአቅም ችግር ነበረባት በማለት የገለጹት ባለሞያው ሶስተኛው ጥጃም ሙሉ አካል ይዞ የተወለደ ቢሆንም በነበረበት ጫና በህይወት መቆየት እንዳልቻለ የገለጹ ሲሆን በአሁን ሰዓት ሁለቱ ጥጃዎችና ላሚቷ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ ብለዋል ሲል ፋስት መረጃ ከአሊቾ ውሪሮ ኮሚዩንኬሽን መረጃውን ተመልክቷል።

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

17 Oct, 05:02


በዘጠኝ ሃገራት የመሬት መንቀጥቀጥ ምሽቱን ተከስቷል

በኢትዮጵያ የምሽቱ መሬት መንቀጥቀጥ ከማጋጠሙ በፊት በየአንድ ደቂቃ ልዩነት ኒውዝላንድ 5:10 ኢትዮጵያ 5:11 ቱክር 5:12 እና ከ 14 ደቂቃ ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ደርሷል ።

በቻይና ፣ ሰሞአ አደሴቶች ፣ ካርማዴክ ደሴት እና አፍጋኒስታን አካባቢዎች ደግሞ ከአንድ እስከ ሁለት ሰአት በፊት መከሰቱን Map of earthquake እና My Earthquake alarts pro አፕ ላይ ተመዝግቧል።

ከነዚህ የመሬት መንቀጥቀጦች በአፍጋኒስታን የተመዘገበው በሬክተር ስኬል 5.9 በመሆን ከፍተኛው ሲሆን በኢትዮጵያ ያጋጠመው በሁለተኛነት ተቀምጧል።

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

16 Oct, 03:26


1፤ የሰሜኑ ጦርነትና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተከሰቱ ግጭቶች ባስከተሉት ጉዳት ላይ ገንዘብ ሚንስቴር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ያስጠናው ኹለተኛው ዙር የዳሰሳ ጥናት፣ በሚንስቴሩ እየተገመገመ እንደሚገኝ ዋዜማ ሰምታለች። የዳሰሳ ጥናቱ ቡድን፣ ጥናቱን አጠናቆ ለሚንስቴሩ ያቀረበው ባለፈው ሐምሌ እንደነበር ታውቋል። ጥናቱ የተካሄደው ከ2015 እስከ 2016 ዓ፣ም ሲኾን፣ ጦርነቱና ግጭቶች በግብርና፣ ቱሪዝምና ኢንዱስትሪ ዘርፎች፣ በኢነርጂና ዲጂታል መሠረተ ልማት፣ በመንግሥት አገልግሎቶችና በመኖሪያ ቤቶች  ላይ በደረሱ ጉዳቶች ላይ ያተኮረ እንደሆነ ዋዜማ ከሚንስቴሩ ምንጮች ሰምታለች።

2፤ ኢትዮ ቴሌኮም ከዛሬ ጀምሮ 10 በመቶ ድርሻውን ለሕዝብ ይሸጣል ተብሎ ይጠበቃል። በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንም ከኩባንያው ድርሻ እንዲገዙ ተፈቅዶላቸዋል። ኩባንያው 10 በመቶ ድርሻውን ለሕዝብ የሚሸጠው፣ በራሱ ቴሌብር መተግበሪያ አማካኝነት ነው። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ኩባንያው ምን ያህል ድርሻዎችን ለሽያጭ እንደሚያቀርብና ያንዱ የአክሲዮን ድርሻ ዋጋ ስንት እንደኾነ አልተገለጠም።

3፤ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ በመንግሥት ኃይሎችና በአማጺው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እንዲኹም በመንግሥት ኃይሎችና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል ከመስከረም 27 ጀምሮ በተካሄዱ ግጭቶች ሰባት ሰላማዊ ሰዎች እንደተገደሉ ከአካባቢው ነዋሪዎች መስማቱን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘግቧል። የአካባቢው ነዋሪዎች የሟቾቹን አስከሬኖች ጥቅምት 2 እንዳገኙ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል። አንድ የአካባቢው አስተዳደር ባለሥልጣን ግን፣ በአካባቢው ምንም ውጊያ የለም በማለት ምላሽ መስጠታቸውን ዘገባው ጠቅሷል።

4፤ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን፣ በአሜሪካ የልማት ተራድዖ ድርጅት ድጋፍ በዘጠኝ ክልሎች ተግባራዊ የሚደረግና ከ5 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት የተመደበለት የአደጋ ሥጋት አስተዳደር ሥርዓት ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል። በ120 ወረዳዎች ተግባራዊ የሚደረገው ፕሮጀክት፣ ከ14 ሚሊዮን በላይ ወገኖችን ማዕከል ያደረገ እንደኾነ ኮሚሽኑ አስታውቋል። ፕሮጀክቱ አደጋ ከመከሰቱ በፊትና ከተከሰተ በኋላ በምን አኳኋን ማስተዳደር እንደሚገባ በተለያየ ሥልጠና የኅብረተሰቡን ንቃተ ሕሊና ከፍ ለማድረግ፣ የአደጋ ማስጠንቀቂያ፣ የምላሽና የትንበያ ሥርዓቶችን ለማጠናከርና አደጋዎችን በራስ አቅም ለመፍታት የሚያግዝ ነው ተብሏል።

5፤ ግብጽ ለሱማሊያ ጦር መሳሪያ መላክ ከጀመረች ወዲህ፣ ኢትዮጵያ በሱማሊያ ግዛት ውስጥ ያላትን የወታደር ብዛት ወደ 22 ሺሕ ማሳደጓን ከምንጮች መስማቱን ጠቅሶ የኢምሬቶች ጋዜጣ ዘ ናሽናል ዘግቧል። በግብጻዊያን ወታደራዊ አማካሪዎች የሚታገዙ የሱማሊያ ወታደሮች፣ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ወታደሮችን ወደ አገሪቱ እንዳታስገባ ለመከላከል ወደ ድንበር መሠማራታቸውን ምንጮች እንደነገሩት ጋዜጣው ጠቅሷል። ግብጽ ባለፉት ሳምንታት፣ ወደ ሱማሊያ ወታደራዊ አማካሪዎችን፣ አሠልጣኞችንና የጸረ-ሽብር ኮማንዶዎችን እንደላከች የጠቀሰው ዘገባው፣ እስከ ታኅሳስ መጨረሻ በሺዎች የሚቆጠሩ ወታደሮቿን ታሠማራለች መባሉንም ገልጧል። ግብጽ፣ ሱማሊያ ውስጥ የወታደራዊ ተልዕኮዋን በማቋቋም ላይ እንደኾነችም ተነግሯል።
ረቡዕ ጥቅምት 6/2017 ዓ፣ም ዋዜማ

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

15 Oct, 17:46


👇 ዝርዝሩ እዚህ አለ👇  
https://youtube.com/live/g8IW_ZdPw1s?feature=share https://youtube.com/live/g8IW_ZdPw1s?feature=share

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

15 Oct, 12:30


በህገ-ወጥ መንገድ ማዳበሪያ ሲያዘዋውሩ በቁጥጥር ስር የዋሉ የ70 ዓመት አዛውንት በእስራትና በገንዘብ ተቀጡ

ሀሰተኛ ሰነዶችን በመጠቀም በህገ-ወጥ መንገድ የአፈር ማዳበሪያ ሲያዘዋውሩ በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉት የ70 ዓመት አዛውንት በእስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ በኦሮሚያ ክልል የሸገር ከተማ ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ ወንጀል ችሎት ወሰነ።

የክልሉ ፍትህ ቢሮ የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ፤ አቶ ተቀባ ማሞ የተባሉ የ70 ዓመት አዛውንት የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 23 ስር የተመላከተውን ድንጋጌ ተላልፈዋል በማለት ክስ አቅርቦባቸዋል።

በክስ ዝርዝሩ ላይ እንደተገለጸው፤ ተከሳሹ ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10:30 ላይ 710 ሺህ 686 ብር የሚገመት 200 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ በተሽከርካሪ ጭነው መነሻቸውን ከአዲስ አበባ ከተማ ከአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በማድረግ ሀሰተኛ ደረሰኝና የይለፍ ሰነዶችን በመያዝ ወደ ደብረ ብርሃን እየተጓዙ እንዳሉ በሸገር ከተማ ኩራ ጅዳ ክ/ከ አካባቢ ሲደርሱ በፀጥታ አካላት ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል።

ተከሳሹ የቀረበባቸው ክስ ዝርዝር በችሎት እንዲደርሳቸውና በንባብ እንዲያደምጡ ከተደረገ በኋላ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የሰጡትን የዕምነት ክህደት ቃል ተከትሎ ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ የሰው ምስክሮችና የሰነድ ማስረጃዎቹን አቅርቦ አሰምቷል።

ፍርድ ቤቱም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መርምሮ ግለሰቡ በተከሰሱበት ድንጋጌ ስር እንዲከላከሉ ብይን የሰጠ ሲሆን፤ ተከሳሹ ግን በተገቢው መከላከል አለመቻላቸውን ጠቅሶ የጥፋተኝነት ፍርድ አስተላልፎባቸዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት በመመርመር እና ተከሳሹ የ70 ዓመት አዛውንት እና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆናቸውን ከግምት አስገብቶ በማቅለያነት በመያዝ በ3 ዓመት ከ11 ወራት ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

በተጨማሪም በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የተያዘው 200 ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ትዕዛዝ ተሰጥቷል።
በታሪክ አዱኛ

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

15 Oct, 08:57


ተረጋግጧል

Major ወደ ገንዘብ የሚቀየረው በመጪው ህዳር ወር መሆኑን የቴሌግራም መስራቹ  Durovs ጓደኛ የሆነው እና የፕሮጀክቱ ባለቤት የሆነው Roxman አሳውቋል።

ምናልባት ያልጀመራችሁ ካላችሁ፣በስልካችሁ ብቻ ገንዘብ መስራት የምትፈልጉ ካላችሁ ሊንኩ ከስር ተቀምጧል፣start በሉት👇👇👇👇👇
https://t.me/major/start?startapp=507730493
👆👆ይፍጠኑ👆👆

Wanaw Media - ዋናው ሚዲያ

15 Oct, 06:48


የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ በላይ እንዳይሆን ተባለ‼️

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ በሚገዙበት እና በሚሸጡበት ዋጋ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ መብለጥ እንደሌለበት አሳሰበ።ብሔራዊ ባንኩ ይህንን በተመለከተ ለንግድ ባንኮች በደብዳቤ ማሳወቁን ገልጿል።

አዲሱ የምንዛሬ ተመን አሰራር ይፋ መሆኑን ተከትሎ በውጭ ምንዛሬ ገበያው ላይ ያሉ ሂደቶችን ሲከታተል መቆየቱን የገለጸው ብሔራዊ ባንኩ፤ የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ መግዣ እና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት በዓለም አቀፍ አሰራር መሰረት መሆን እንዳለበት አመልክቷል።

በመሆኑም የውጭ ምንዛሬ መግዣና መሸጫ መካከል ያለው ልዩነት ከሁለት በመቶ በላይ መሆን እንደሌለበት አስታውቋል።

አሁንም ቢሆንም ባንኮች የምንዛሬ መግዣ እና መሸጫ ዋጋቸውን በራሳቸውና ከደንበኞቻቸው ጋር ባላቸው ስምምነት ማድረጋቸውን እንደሚቀጥሉ ጠቁሟል።

ንግድ ባንኮች የምንዛሬ መግዣ እና መሸጫ ዋጋቸውን በተናጠል በየቀኑ ማሳወቃቸውን መቀጠል እንዳለባቸው ጠቅሶ፤ ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ሽያጭ ጋር በተያያዘ የሚጠይቋቸውን ኮሚሽኖች ከምንዛሬ መሸጫ ጋር ሳይሆን በተናጠል ለደንበኞቻቸው እንዲያሳውቁሞ አዝዟል።

እስካሁን በነበረው አሰራርም ንግድ ባንኮች የምንዛሬ መሸጫ ዋጋቸውን ከኮሚሽኑ ጋር ደምረው ያስታውቁ እንደነበር አስታውሶ፤ ንግድ ባንኮች ሁለቱን ጉዳዮች እስከነገ ባለው ባለው ጊዜ ተግባራዊ ሊያደርጉት ይገባል ብሏል።