ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት @mstaketsehay Channel on Telegram

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

@mstaketsehay


ይህ ቻናል የምሥራቀ ፀሐይ አቡነ ቶማስ መታሰቢያ የመጻሕፍት ትርጓሜ ጉባኤ ቤት በቤተ ከርስቲያን ዙሪያ ማስተማሪያና ማወያያ ገጽ ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት (Amharic)

እንኳን ለምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት ከተማህለህ! በዚህ ትርጉም ይህ ቻናል የምሥራቀ ፀሐይ አቡነ ቶማስ መታሰቢያ የመጻሕፍት ትርጓሜ ጉባዔ ቤት በቤተ ከርስቲያን ዙሪያ መወያያ ገጽ አለ። ይህ ቤት የምሥራቁ ፀሐይ ድንቅ ውድ እና የርስቲያን የክልላዊ እምነት ለሚሆን ነው። የምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት 'mstaketsehay' የታወከችው ከተማ ለተከበረው ሰው እና ታላቅ አስተሳሰብ እንደሆነ አገልግሎት እንዲሰጡ ነው። የግርድ ምንጭ አለው እና የፀሐይን ቤተሰብ በዚህ እድሜው ለማክበር ከብርሃኑ በታች ያላችሁት ሌሎች አስተዳደሮ ቦሌና መዝግብ ይችላሉ።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Feb, 10:53


    የሞት እንግድነት እንዴት ተለመደ?
መጽሐፍ የሚለው ሞት እንደማይለመድ እና ሁልጊዜም ሐዲስ እንደሆነ ነው።
በእኛ ሀገር ያለው ሞት ግን የተለመደ የቅርብ ዘመድ የቅርብ ጎረቤት ከሆነ ዘገየ።
ጧት ማታ ስለ ሚጎበኘን አስፈሪነቱን ተላመድነው።
የሞት መልእክተኞች ሹማምንት ሁል ጊዜ ሥራውን ስለ ሚያሳልጡለት እንግድነቱ ተረስቶ ሁል ጊዜም የሚጠበቅ የግድ ዘመድ ሁኗል።
ጧትም ሞት፣ማታም ሞት፣በየሰዓቱ ሞት፣በየሸንተረሩ ሞት፣ሞት ሞት..በየቀኑ ሞት የማይሰማበት መንደር ስለሌለ የጆሮ ዘመድ ሁኖ ግብሩ ተለምዶ ሁሉን ድንዙዝ አደረገው።
ይልቁንም ይሄው ሞት በንጻሓን ላይ በትረ ሥልጣኑን ስለሚያጸና እኖራለሁ ባይ እስኪታጣ ቅርብ ዘመዱን በቀቢጸ ተስፋ ባሕር እያሰጠመው ነው።
ሞት አዳማዊ ርሥት ቢሆንም የሚወረሰው በድንገት እንደ ሌባ አመጣጥ ነበር።
አሁን አሁንማ በዕቅድ በክፉዎች ፈቃድ በትውልድ ቅነሳ ምክንያት ርሥትነቱ በድንገት ሳይሆን በልምምድ ሁኗል።
ትልቁ ድንዛዜ ጥፋትን መለማመድ ነው።"ከሰይጣን ልማድ ይከፋል"እንደ ሚባለው ከክፋት ሁሉ ክፋት የልምምድ ጥፋት ነው።
መጽሐፍ እንደ ሚለው ለሁሉም ጊዜ ነበረው፦"ለመወለድ ጊዜ አለው ለመሞትም ጊዜ አለው።"መክ.፫፥፪ እንዲል።
ከእኛ ሀገር ግን ለመወለድ እንጂ ለመሞት ጊዜ የለውም።
ባላሰቡት ዕለት ባልጠረጠሩት ሰዓት ያለ ጊዜው በጥፋት ልምምድ ሰው ሁሉ ይሞታል።
ይህ ጥፋት፣ይህ መቅሰፍት፣ይህ የሞት ዕቅድ፣ይህ ድምሳሴ..የሚለወጠው እንዴት ነው?
እኛ ግን ከሐዋርያው ጋራ እንዲህ እያልን እንዘምራለን፦"አዎን፥ ሙታንን በሚያነሣ በእግዚአብሔር እንጂ በራሳችን እንዳንታመን፥ እኛ ራሳችን የሞትን ፍርድ በውስጣችን ሰምተን ነበር።እርሱም ይህን ከሚያህል ሞት አዳነን  ያድነንማል።፪.ቆሮ.፩፥፱

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Feb, 10:39


          የክርስትና ሕይወት የመስቀል ፍቅር ነው።
እያንዳንዱ ክርስቲያናዊ የሕይወት ልምምድ የመስቀል ፍቅር መገለጫ ነው።
እርሱ ለሰው ፍቅር ሲል አዳማዊ ባሕርይን ተዋሕዶ ግብረ ሰብእን ሂደት በሂደት እስከ ዕለተ ዓርብ እንደ ገለጸልን እኛም መንፈሳዊ የጥምቀት ልደትን ገንዘብ አድርገን መስቀላዊ ግብርን ሂደት በሂደት እንለብሰዋለን።
ከአምላክ ሰው መሆን በላይ ፍቅር እንደሌለ የመስቀል ሕይወትን ከመሸከም በላይም ፍቅር የለም።
እርሱ ወደ መስቀል ከፍ ሲል እኛንም አብሮ ሰቅሎናልና መስቀሉ መስቀላችን ነው።"እኔም ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደ ሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ።"ዮሐ.፲፪፥፴፪ እንዲል።
መስቀሉን መስቀል ካደረግነ ሕይወቱንም ሕይወት እናደርጋለን።"ልጆች ከሆንን ወራሾች ደግሞ ነን ማለት የእግዚአብሔር ወራሾች ነን አብረንም ደግሞ እንድንከበር አብረን መከራ ብንቀበል ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን።"ሮሜ.፰፥፲፯ እንዲል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Feb, 10:29


የተማሪዎቼ ሀኪም ትሁቱ አገልጋይ።
ብዙ ጊዜ በጉባኤ ቤት ደረጃ ደቀ መዛሙርቱ ከሚቸገሩባቸው ነገሮች አንዱ ደቀ መዛሙርቱ ሲታመሙ ህክምና ማግኘት አለመቻላቸው ነበር።
ዶክተር አንዷለምና ጓደኞቹ ግን አይደለም የማከሚያ ቦታቸው ሂደን ይቅርና ወደ ጉባኤ ቤት በመምጣት ያክሙን ነበር።
መነኮሳትን እና ደቀ መዛሙርትን በሙያችን የማከም ሀላፊነት አለብን ብለው ባላቸው ጊዜ በየጉባኤው እየዞሩ የድርሻቸውን ተወጥተዋል።
የጤና አጠባብቃችን ምንም መሆን እንዳለበት በተወደደ ጊዜያቸው ጉባኤ ቤት እየተመላለሱ አስተምረውናል።
ሰማዕቱ ዶክተር ደግሞ የተለየ ትሁት ወንድም ነበረ።ተማሪ ታሞብኛል ምን ይሻላል? ስለው  ወደዚህ ከመምጣቱ  በፊት በስልክ ልጠይቀው አገናኘኝ ይለኛል።ከዚያም ወደ ሆስፒታል የሚያስሄድ ጉዳይ ከሆነ በዚህ ቀን ይምጣ ይላል።በሌለ ጎኑ ደቀ መዛሙርትን የሚያክምልን ወጪው በራሱ ሁኖ በነጻ ብቻ ነው።
ይሄንን ትሁት ወንድም ማጣት እጅጉን ያማል፣ያበሳጫል፣ያሳዝናል።
ሃይማኖተኛ እና እውነተኛ ሰዎች ታሪካቸው ብዙ እድሜያቸው ግን አጭር ነው።
ትንሿን እድሜያቸውን ለእውነት እና ለቅንነት ስለሚኖራት ትርፍ ያልተሠራበት እድሜ የላቸውም።
በቅንነት እና በአገልግሎት ሲፋጠኑ በግፍዕ የሚሞቱ የሕያዋን ሰማዕታት ደማቸው እንደ አቤል እና ዘካርያስ ደም ግፈኞቹን ይካሰሳል።
ፍትሀ እግዚአብሔር በጊዜው ጊዜ መድረሷ አይቀርምና ግፈኞች ለንጹሓን ሰማዕታት በቀዱት የግፍዕ ፅዋ መጠጣታቸው አይቀርም።
ከጥንት ጀምሮ የእግዚአብሔር አሠራሩ ልሚዱ እንዲህ ነው፦ለጻድቁ ፈርዶ ዋጋውን በኃጥኡ ፈርዶ ፍዳውን ማምጣት።
"እርስዋ እንደ ሰጠች መጠን ብድራት መልሱላት እንደ ሥራዋም ሁለት እጥፍ ደርቡባት በቀላቀለችው ጽዋ ሁለት እጥፍ አድርጋችሁ ቀላቅሉባት።"ራእ.፲፰፥፮ እንዲል።
የዶ/ር አንዱዓለምን ዳኘን ሕጻናት ልጆቹን ማሳደግ አለብን።
ጓደኞቹ ለዚሁ ዓላማ በከፈቱት ቁጥር የድርሻችንን እንወጣ።
Account Holder Names:
Dr. Hailemariam Awoke
Dr. Amsalu Worku
Dr. Mequanint Yimer
Bank: Commercial Bank of Ethiopia (CBE), Bahir Dar Branch
Account No:
1000676116978
© College of Medicine and Health Science, Bahir Dar University

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Feb, 07:48


ሃይማኖተኛ እውነተኛ ሰዎች ታሪካቸው ብዙ እድሜያቸው ግን አጭር ነው።
ትንሿን እድሜያቸውን ለእውነት እና ለቅንነት ስለሚኖራት ትርፍ ያልተሠራበት እድሜ የላቸውም።
በቅንነት እና በአገልግሎት ሲፋጠኑ በግፍዕ የሚሞቱ የሕያዋን ሰማዕታት ደማቸው እንደ አቤል እና ዘካርያስ ደም ግፈኞቹን ይካሰሳል።
ፍትሀ እግዚአብሔር በጊዜው ጊዜ መድረሷ አይቀርምና ግፈኞች ለንጹሓን ሰማዕታት በቀዱት የግፍዕ ፅዋ መጠጣታቸው አይቀርም።
ከጥንት ጀምሮ የእግዚአብሔር አሠራሩ እንዲህ ነው።ለጻድቁ ፈርዶ ዋጋውን በኃጥኡ ፈርዶ ፍዳውን ማምጣት።
"እርስዋ እንደ ሰጠች መጠን ብድራት መልሱላት እንደ ሥራዋም ሁለት እጥፍ ደርቡባት በቀላቀለችው ጽዋ ሁለት እጥፍ አድርጋችሁ ቀላቅሉባት።"ራእ.፲፰፥፮ እንዲል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Feb, 07:38


ሞት የማይቀር አዳማዊ ርሥት ቢሆንም ፍትህ አልባ ሞት ግን ለቋሚ ከልብ የማይጠፋ አረመጨት ነው።
ቅዱሳን ሰማዕታቱ ለእውነት መሥክረው አልፈዋል።
በክፉ አድራጊ መሪዎች እና ሃይማኖት በሌላቸው የሃይማኖት አባቶች መከራ ተቀብለው ሞታቸው ወደ ዘለዓለማዊ ሕይወት ተቀይሯል።
ታሪካቸውን የምንዘክር እኛም መንገዳቸው መንገዳችን ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Feb, 22:33


             ዮሴፍን የሸጠው ማን ነው?
እንደሚታወቀው ዮሴፍ የተሸጠው  በወንድሞቹ ነው።ነገር ግን ዮሴፍን ወንድሞቹ ምክንያት ቢሆኑም ወንድሞቹ እንደሚሸጡት ባለመጠርጠሩ ነው።
ይልቁንም ባሪያ ነው ብለው ለምድያማውያን ነጋዴዎች ሊሸጡት፦ " ኑ ለእስማኤላውያን ነጋዴዎች እንሽጠው።"ዘፍ.፴፯፥፳፯ ብለው
ሲዋዋሉበት እኔ ወንድማቸው ነኝ እንጂ የሚሸጥ ባሪያ አይደለሁም የአብርሃም፣የይስሐቅ፣የያዕቆብ ልጅ ነኝ ብሎ ቢናገር ኑሮ ባልተሸጠም ነበር።ዮሴፍ በዝምታ በመሸጡ ምክንያት እግዚአብሔር የመገፋቱን ዋጋ ባያስቀርበትም በመሸጡ ወንድሞቹ ብቻ አይወቀሱም እርሱም  ወንድሞቹ እንደ ጠሉት እያወቀ ባለመጠርጠሩ ሊጠየቅ ይገባዋል።
እኛ ኦርቶዶክሳውያንም የምንመስለው ዮሴፍን ነው።ባለመጠርጠራችን እና ባለመናገራችን ምክንያት ወንድም ዘመድ ካልናቸው ሰዎች የተነሣ ለሥሁት ርዕዮተ ዓለም እና ጨቋኝ ተጨቋኝ ትርክት ልንሸጥ ችለናል።
ዮሴፍ የመናንያን ምሳሌ ሁኖ ለጽድቅ ለትሩፋት ሲል ተሸጠ።እኛ ለዚህ ሁሉ ሥቃይ የተሸጥነው ለምን ብለን ነው?
ከሁሉም መከራ የከፋው ለምድያም ነጋዴዎች መሸጥ ነው።ከነጋዴ ወደ ነጋዴ ያለ ዕረፍት የፈርዖን ባሪያ እስኪሆኑ ድረስ በቃ መሸጥ ነው መሸጥ ነው።
የተሸጠ ሰው ሰው ደግሞ፦ ሀገር የለው፣ዘመድ የለው፣ታሪክ የለው፣መብት የለው፣ዕረፍት የለው፣..ሁለንተናውን የተነጠቀ ምስኪን ነው የሚሆነው።የራሴ የሚለው ምንምም ሀብትና ሰውነት የለውም።
"ውረድ ከማማ፣ውጣ ከአውድማ፣ንቀል ከባድማ፣ተሸጥ በሸማ" እየተባለ እንደ ጥሬ ዕቃ ገበያ በደራ ቁጥር ይሻሻጡታል ይለዋወጡታል እንጂ ማንም የሚያከብረው የለም።በመጨረሻም፦"ዮሴፍ ለባርነት ተሸጠ።"መዝ.፻፬፥፲፯ መሸጡን ግን በጽኑ ትጋት በብዙ መከራ ወደ ክብር ቀየረው።
በኢትዮጵያ ያለን ኦርቶዶክሳውያንስ?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Feb, 15:37


ያለ ሃይማኖትና እምነት የውስጥ ሰላም አትገኝም።
ሃይማኖትም እምነትም የሌለው ሰው በውስጥ በአፍአ የታወከ የተረበሸ ነው።
ሃይማኖት እና እምነት ያለው ሰው ግን ከሰው የሚገኘው አፍአዊ ሰላሙን ቢያጣም እንኳን ከእግዚአብሔር የሚገኘው ውስጣዊ ሰላሙ የተጠበቀ ነው።
በልብ ውስጥ ያለው የእምነት ዕረፍትን መንጠቅ የሚቻለው አፍአዊ ሰው የለም።
በእምነታቸው ምክንያት በውስጣቸው አድሮ ያለው ተስፋ የማይናወጽ ጽኑዕ ማረፊያቸው ነውና።ቅዱስ ሐዋርያ፦"አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።"ፊል.፬፥፯ ብሎ እንደ አስተማረን።
በዚህ አውሎ ነፋስ በሆነው የነውጽታ የመከራ ዓለም ውስጥ ያለ ውስጣዊ ዕረፍት መኖር በጣም ከባድ ነው።
አንድ ምድራዊ ተስፋ ብቻ ያለው ሰው ያችኑን አንዲቷን ጊዜያዊቷን ተስፋውን ክፉ ሰዎች ሲነጥቁበት በምንኛው ተስፋው ይጽናናል?
ምድራዊ ተስፋ ብቻ ያለው ሰው አንድ ሥጋዊ ማያ ብቻ የለው ፍጡር ነው።
በነፍስ በሥጋ በተዋሕዶ የሚያስብ ተስፋ የሚያደርግ ሰው ግን አንዱን ምድራዊውን ቢነጠቅ"በሰው እጅ የማይናኝ እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ያዘጋጀው ዓይን ያላየው ጆሮ ያልሰማው" ጽኑዕ ተስፋ አለው።፩.ቆሮ.፪፥፱
ትንሣኤ ሙታንን እና ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን የማያምን ሰው ግን ምንም አይነት ማረፊያ ህሊና የለውም።
በሥራው ሁሉ እንደ ባሕር ሞገድ የታወከ ነው እንጂ።
አንድ ተስፋ ብቻ የውስጥ ሰላምን አያስገኛትም።
የውስጥ ተስፋ ያለው ሰው ግን አንዱን ቢያጣ አንዱን አያጣም።
ክፋቱ ከሁለቱም ተስፋ ከተሰደዱ ነው።
የውስጥ ሰላም የውስጥ ዕረፍት የሌለው ሰው ከነዚያችውም ሰላሙን አጥቶ ለቀቢጸ ተስፋ የተጋለጠ ነው።
ስለሆነም በክፉ መሪዎች ምክንያት ተስፋችንን እንዳናጣ የእምነት ማሰቢያ አእምሯችንን መጠበቅ አለብን።
የእምነት ማሰቢያ አእምሮ የተጠበቀለት ሰው ትንሣኤ ሙታንን እንደሚያምን ሁሉ ትንሣኤ ጊዜንም አምኖ ለእውነተኛ ዕረፍት ይሠራል።
"ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤በተስፋ ደስ ይበላችሁ።"ሮሜ.፲፪፥፲፩

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Feb, 15:15


     ኦርቶዶክሳውያን አስተማሪዎች እና አባቶች፦እንዲህ ቢሆኑ ጥሩ ነው።ኦርቶዶክሳዊነትን ለማስቀጠል የክርስትና አደራን በሐዋርያዊነት ጠብቀው አስተምረው ለትውልድ የሚያቀብሉ አስተማሪዎች፦
=-ጥንቁቅ፣ጭምጥ፣ቁጥብ፣ሥውር፣ግልጽ የተራራ መቅረዝ መሆን አለባቸው።
=-በአርአያነት የሚያስተምሩ አባቶች፦ ለእግዚአብሔር መታመን፣ኦርቶዶክሳዊ ነገረ ድኅነትንም ማመን፣ለሚያስተምሩት ምእመን በአባትነት መታመን መቻል አለባቸው።
=-ኦርቶዶክሳዊ አስተማሪዎች፦ግልጽ በሆነ የወንጌል ራዕይና የሐዋርያዊ አስተምህሮ ፍኖተ-ድኅነት መጓዝ መቻል አለባቸው።
=-ኦርቶዶክሳውያን አስተማሪዎች፦ በተገለጸ ክርስቲያናዊ የወንጌል ዕቅድ እና ዘመኑን በተላበሰ የትኩረት አቅጣጫ ወንጌልን እያስተማሩ መመራት አለባቸው።
=-ኦርቶዶክሳዊ አስተማሪዎች፦እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ቅን እና አገልጋይ መስቀል ተሸካሚ መሆን አለባቸው።
=-ኦርቶዶክሳዊ አስተማሪዎች፦ በእግዚአብሔር አማኝ፣ሁል ጊዜ የሚማር ትምህርት መማርን ያላቆመ፣ወቅቱን ሁኔታውን የተረዳ፣እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ የሰማህትነት ህሊናን የተላበሰ፣እንደ ሰሎሞን ፍርድን ያስተካከለ፣መሆን አለባቸው።
=-ኦርቶዶክሳዊ አስተማሪዎች፦በምንም አይነት ምድራዊ ጥቅም የወንጌልን እውነት መባያ የማያደርጉ፣በመስቀሉ የማይቆምሩ፣ምላስ አስልተው የማይሸነግሉ፣የሚሉትን የሚያስተምሩትን የሚኖሩ፣አውግዠ እስክመጣ እየፈጨሽ ቆይኝ የማይሉ፣በዓለም ቢኖሩም የምናኔ ሕይወትን የተላበሱ፣እንደ ኤልያስ እንደ ዮሐንስ ለእውነት የሚኖሩ፣የአክዓብ የሄሮድስን ግርማውን ማማውን አይተው የማይፈሩ..መሆን አለባቸው።
=-መንፈሳዊ አስተማሪዎች፦ትምህርት፣ዕውቀት፣መረዳት፣ኅብረት፣ተግባር፣ተስፋ..ያላቸው የሐዋርያት ልጆችና ተከታዮች መሆን አለባቸው።
እንዲህ እንሆን ዘንድ የቅዱሳን አምላክ ይርዳን።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Feb, 12:41


               ቅዱሳት መጻሕፍት፦
ሁሉም ሰው እንደ አቅሙ ቅዱሳት መጻሕፍትን ያነብ ይሆናል።ስናነባቸው በምን የመረዳት ደረጃ ውስጥ ሁነን ነው? ንዑስ መግቢያ የሚሆኑ መሠረተሀሳቦች ከዚህ ታች ተቀምጠዋል፦
[  ] ፩.በንባብ፣
[  ] ፪.በትርጉም፣
[  ] ፫.በአረዳድ፣
[  ] ፬.በምሥጢር፣
[  ] ፭.በሕይወት፣
[  ] ፮.በተስፋ..የከበሩ ናቸው።
በንባብ የከበሩ ናቸው፦ማለት ቃለ እግዚአብሔር ረቂቅ ሁኖ ሳለ በመጽሐፍ ከመጻፉ የተነሣ በዓይን የሚታይ በጆሮ የሚሰማ ሁኗል።ይህ ቅዱስ ቃል የሚነቡብ የሚታይ እንደመሆኑ መጠን የላይ የላዩ ንባብ ዘር ይባላል።
[  ] በትርጉም የከበሩ ናቸው ማለትም፦ ሁሉም የቅዱሳት መጻሕፍት ንባብ ትርጉም የሚያሻው እንደመሆኑ መጠን በቅዱሳት መጻሕፍት ላይ የተቀመጠውን ሀሳበ እግዚአብሔር ለማወቅ የግድ ትርጉም ያስፈልጋል።እየተነበበ የሚተረጎም ቃለ እግዚአብሔር ዋና መሠረተ ሀሳቡ ሲተረጎም ለሰሚ ልቡና የተረዳ ይሆናል።
በአረዳድ የከበሩ ናቸው ማለትም፦ ተነበው እና ተተርጉመው ጥንተ መሠረቱን ሳይለቁ ፈቃደ እግዚአብሔርን የምንረዳባቸው ናቸው ማለት ነው።የቅዱሳት መጻሕፍት አረዳድ ከሐዋርያት ጀምሮ የመጣውን ኅብረታዊ መሠረተ ሀሳብ ይዘው የሚቀጥሉ ናቸው እንጂ ዘመን አመጣሽ ሁነው መረዳት አይችሉም።
[  ] በምሥጢር የከበሩ ናቸው ማለትም፦የቅዱሳት መጻሕፍት ዋና አረዳድ ለቅዱሳን የተገለጠውን ሃይማኖት እና የድኅነት ምሥጢርን መጠበቅና ለሰው ሁሉ መስጠት ሲችሉ ነው።የቀለም ሠረገለ መዳረሻው ወደ ትክክለኛ ምሥጢረ ድኅነት መሆን አለበት።
በሕይወት የከበሩ ናቸው ማለትም፦ተነበው፣ተተርጉመው፣ተረድተው፣ተመሥጥረው ሰውን ሁሉ በትክክለኛው የወንጌል ሕይወት ማኖር ይችላሉ ማለት ነው።የቅዱሳት መጻሕፍት ዓላማ ሰምቶ ለሚተገብራቸው ሁሉ ሕይወትን ማሰጠት ነውና።የሰማነው ያወቅነው ቃል በሕይወት ሲተረጎም የሚኖር ቃል ይሆናል እንጂ የሚነበብ ቃል ብቻ አይሆንምና።
[  ] በተስፋ የከበሩ ናቸው ማለትም፦በዚህ ዓለም የቅዱሳት መጻሕፍትን ሀሳብ ጠብቆ የኖረ ሰው ሁሉ ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን ማግኘቱ አይቀሬ ነውና።ከሚታየው በኋላ፣ከሞት በኋላ፣ከትንሣኤ ዘጉባኤ በኋላ፣ የሚገኘውን ጸጋ ክብር ማግኘት የሚቻለው ዛሬ በቅዱሳት መጻሕፍት የተነገረውን ተስፋ ተረድቶ በመጠበቅ ላይ ጸንቶ በኖር ነውና።
ቅዱሳት መጻሕፍትን ስናነብ ባጭሩ መታሰብ የሚገባቸው ቅደም ተከተሎች እነዚህ ናቸው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Feb, 12:08


             "በጎች ምን አደረጉ?"
ሳር ነጭተው ውኀ ተጎንጭተው የሚኖሩ በጎች ምን አድርገው ነው የሚታረዱት? ከቀበሮ የጠበቀ ያሰባ ያረባስ ይሁን የድካሙን ዋጋ ለማግኘት ጸጉራቸውን ለልብስ፣ቆዳቸውን  ለነት፣ሥጋቸውን ለጥብስ ብሎ ያርዳቸዋል።
ያልደከመባቸው ምንደኛ ግን ያለፍትህ ሳር ሳያበላ፣ውኀ ሳያጠጣ፣ከቀበሮ ከአውሬ ሳይጠብቅ የሚያርዳቸው የሚያወራርዳቸው በምን ህሊናው ነው?
ምንስ የዋህ በግ ቢሆኑ የህሊና ቸርነት የተፈጥሮ ርህራሄ አያስፈራውም እንዴ?
በቃ በግ ከሆኑ ዘንድ ዘንግ አቅንቶ ዳኛ አውጥቶ የሚከራከርላቸው የለም ተብሎ ይታረዱና ይበሉ ይባላል ወይ?
ቅዱስ መጽሐፍ ፦"ጻድቅ ሰው ለእንስሳው ነፍስ ይራራል።የኀጥአን ምሕረት ግን ጨካኝ ነው።"ምሳ.፲፪፥፲
ጻድቅ ሰው ስንኳን ለሰው ለእንስሳው ይራራል  ነበር የሚለው።ለበግ የሚራራላት ማን ነው?
እረደው እረደው ሥጋውንም እንብላው ብቻ ከሆነ ነገሩ እንዴት ነው? ቅዱስ መጽሐፍ ስለ ክርስቶስ ሲናገር፦"ስቀለው ስቀለው እያሉ ይጮኹ ነበር።"ሉቃ.፳፫፥፳፩ እንዳለ።
በጎችን እንብላቸው እንብላቸው እያሉ የሚጮሁ በዝተዋል።
የበጎች መልካም እረኛማ ቢኖራቸውማ፦"እነሆ እኔ በድያለሁ ጠማማም ሥራ እኔ አድርጌአለሁ እነዚህ በጎች ግን እነርሱ ምን አደረጉ? እጅህ በእኔና በአባቴ ቤት ላይ እንድትሆን እለምንሃለሁ።"፪ሳሙ.፳፬፥፲፯ ብሎ ወደ እግዚአብሔር ይለምንላቸው ነበር።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Feb, 07:50


በዚህ ዘመን ሰማዕትነትን በህሊና፣በትምህርት፣በኑሮ መለማመድ ግድ ነው።
ያለዚያ ሞታችን የዘለዓለም ሕይወትን የሚያሳጣ ደመ ከልብ ነው የሚሆነው።
ኦርቶዶክሳዊ ጠልነት ለምልሞ፣አብቦ፣አፍርቶ፣አሁን እየታጨደ ስለሆነ በዚህ ህሊና ጠል በሆነ ስም የተፈረጀ ክርስቲያን ሞቱ ከውሻ ሞት ያነሰ ነው።
አሁን በዚህ ሰዓት ለእኛ ያለነው እኛና እግዚአብሔር ብቻ ኑን።
እንዲህ ሆንሁኝ ተብሎ ለማን ዳኛ መናገር ይቻላል? የለም።
ስለዚህ ፍትህ ርትዕ ሰፍኖ ክርስቲያንነት እንደ ሰው እስኪታይ ድረስ በቅዱሳን ሰማዕታት ህሊና ሁኖ መኖር ጥሩ ነው።
ክርስትና ከባለቤቱ ከክርስቶስ ጀምሮ በምድር መስቀለኛ መከረኛ ቢሆንም የተለዩ ዘመነ ሰማዕት የሚባሉ ዘመኖች እንደነበሩ አሁንም እንደዚያ ያለ ዘመን ነው።
የምድር ሀሳሩን በሰማዩ ክብር መለወጥ የሚቻለው በክርስቶስ መስቀል ነውና መዘናጋት አይገባም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Feb, 07:25


መጻሕፍት የህሊና ምግቦች የአእምሮ ማሳደጊያዎች ናቸው።
በተለይም በመጻሕፍት ቤት ለሚማር ደቀ መዝሙር አይነተኛ ፈውሶች ናቸው።
ደቀ መዝሙር አስተሳስብን፣አነጋግርን፣አሠራርን የሚያረታው በትምህርት እና በንባብ ነው።
ከጫካ ገብተው አንድ ሐረግ ቢስቡ ብዙ እንደሚሰበስቡ ከመጻሕፍት ዓለምም አንድ ምሥጢር ይዘው ሲመራመሩ ወደ ብዙ ዓውደ ንባብ እየሳበ ያስገባል።
ደቀ መዝሙር ለሰው የሚተርፍ ዕውቀት መሸመት የሚችለው በንባብ ነው።
የማያነብ ሰው የተለጎመ የተሸፈነ ነፋስም ውኀም የማይገባበት ዝግ ማድጋ ነው።
ሁል ጊዜ ጽሙድ እንደበሬ ቅኑት እንደ ገበሬ ሁኖ የሚያነብ ደቀ መዝሙር ግን እንደ ቃና ወይንጠጅ የተለወጠ የጣፈጠ ሀሳብ ትምህርት የሚጨመቅበት የወይን ጠጅ ጋን ነው።
ከዚያ ጠጅ ሁሉም መቅመስ እንደሚመኝ ያነበበ የተማረ ደቀ መዝሙርም ሲያስተምር ለጆሮ የሚመጥን ለነፍስ የሚጠቅም ምክርን ይሰጣል።አልፎት የሚሄድ የለም ሁሉም ትምህርቱን ለመቅመስ ይጓጓል እንጂ።
አዲሱ ጉባኤ ቤት ለደ መዛሙርት ማስያ መሣያ የሚሆኑ መጻሕፍትን ለግሱኝ እያለ ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

02 Feb, 09:56


ሰው የሚሠራው እንጂ የሚያስበው ለሌላ ሰው አይታወቅም።
ምንም አየይነት መልካም ሀሳብ የሚያስብ ሰው በማሰቡ ብቻ በተግባር ካልገለጸው ማን ያውቅለታል?
እኔኮ መልካም ነው የማስበው? የሚሉ ሰዎች ቢኖሩ ማሰባቸው መልካም ቢሆንም በውስጡ መልካም ማሰቡ ለሌላው ምን ይጠቅመዋል?
ለሰው የማይተራፍ መልካምነት ምን አይነት መልካም ነው?
መልካም ሀሳብ ለሰው መትረፍ ከቻለ ክርስቶስን የመምሰል አስተሳስብን ያለማምዳል።
"እናንተም ከሚያስደነግጥ ነገር አንዳች እንኳ ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ ልጆችዋ ናችሁ።"፩.ጴጥ.፫፥፮

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

02 Feb, 03:51


 ያመኑትን ካልመሠከሩ አማኝ አይባሉም።
ሁሉም ቅዱሳን የእግዚአብሔር ምሥክሮች ናቸው።አምልኮቱን ሳይመሠክሩ ወደ ቅድስና መዓርግ የወጡ የሉም።ዕለት ዕለትም ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ማመስገናቸው የምስጋና ምሥክርነትን እየገለጹ ነው።
ጥንት በሥነ ፍጥረት ጊዜ በሰማያትም"ንቁም በበህላዌነ-በእያለንበት እንጽና"በሚለው ገብርኤላዊ ቃል መሠረት በፍጹም ልቡና ፍጹማን ምሥክሮች ሁነዋል።
በዚህ የፍዳ ዓለምም ከአዳም ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ ባለው የእግዚአብሔር ወገኖች የሚታወቁት በምሥክርነታቸው ነው።ኖኅ፣አብርሃም፣ሎጥ..
ስትመስሉ እኛን ምሰሉ ካለዚያ ከሀገራችን ንቀሉ ስትወዱ እኛን ውደዱ ካለዚያ ከሀገራችን ወግዱ"እየተባሉ አይተገፉ በእመነት ጸንተው ኑረዋል።
የሚያምኑትን ካልመሠከሩት ምኑን አማኝ ይባላሉ? ማመን ማለት ቅሉ አምልኮቱን መግለጽ መመሥከር ነውና።
ዛሬ በእኛ ላይ ሊፈጸም የሚገባው ምሥክርነቱም ባጭሩ፦
፩. በቅድምና የነበረውን፣ዓለሙን አሳልፎ የሚኖረውን፣በኋላ ዘመን ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር ከኢምንት ወደ ምንት አምጥቶ የፈጠረውን ፣በሦስት አካል የተገለጠውን
        አንድ አምላክ እግዚአብሔርን  ማመን  መታመን  እና ሀልወቱን አምልኮቱን መመሥከር ነው።ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት፦"በነገሥታት ፊት ምስክርህን እናገራለሁ አላፍርምም።"መዝ.፻፲፰፥፵፮ ብሎ እንደነገረን።
፪. እግዚአብሔር በልብ የመከረውን በነቢያን ያናገረውን ለመፈጸም ከሦትቱ አካላት አንዱን የእግዚአብሔር ቃልን ሰው መሆን እና የሰውን ልጅ ድኅነት ማመን  መታመን  እና መመስከር ነው።ሮሜ.፲፥፱
፫. በአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ህሊና ውስጥ ሁነው ከሃይማኖት ሊያወጣ ከቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኅብረት አንድነት ሊነጥል የሚችል (ኅጢአት ፣ በደል) እና
      የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኅብረት እንዳትቀጥል  ሊያደርግ ከሚችል ማንኛውም  ነገር (ፍልስፍና   ደርጅት አስተሳስብ ሹማምንት) ጋር እንደ አመጣጡ ለመመለስ  የሚደረግ አካላዊ አእምሯዊ ተጋድሎ ሰማዕትነት ምሥክርነት ይባላል።
ሰማዕትነቱ በሁለት መንገድ ይፈጸማል።አንዱ በሕይወት በኑሮ በምሥክርነት ነው።እንዲህ ያለው ዘእንበለ ደም ሰማዕት ይባላል።
ሁለተኛው እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ በሰይፍ ተመትረው በኩላብ ተሰቅለው.. ደማቸውን አፍስሰው የሚቀበሉት ሰማዕትነት ነው።
በዚህ ዓለም በሃይማኖት ጸንቶ ምንም ይሁን ምን ማንም ሰው በሃይማኖቱ ምክንያት ከሞተ ሰማዕት ነው።
በዘመናችን ያሉ ሰማዕታትን በሃይማኖታቸው ምክንያት በሥሁት ትርክት ተጠልተው መከራ ቢቀበሉ ሰማዕታት ናቸው።
ከላይ ካሉት  የመከራ አይነቶች ያልተቀበሉት የለም ማለት ይቻላል፡፡በክርስቶስ ላይም፣በሐዋርያትም የሆነው እንዲህ ያለ መገፋት ነውና።ቅዱስ ወንጌል፦"በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።"ማቴ.፲፥፳፪ እንዳለ።
በሃይማኖት ኦርቶዶክሳዊ ሰው ሁሉ ሁል ጊዜም ምሥክር መሆኑን መዘንጋት የለበትም።
የእግዚአብሔር ሕጉ ወንጌል ወደሚመጣው ትውልድ ታልፍ ዘንድ በብዙ መንገድ ምሥክር መሆን  ግድ ነው።
[  ]  ወይ በጸሎቱ ምሥክር መሆን።
[  ] ወይም በሕይወቱ ሰማዕትነትን ተቀብሎ ምሥክር መሆን።
[  ]  ወይም በጉልበቱ ምሥክር መሆን።
[  ] ወይም በልዩ ልዩ ትሩፋቱ ምሥክር መሆን።
[  ]  ወይም በገንዘቡ ምሥክር መሆን።
[  ]  ወይም በዕዉቀቱ ምሥክር መሆን።
[  ]  ወይም በሥልጣኑ  ምሥክር በመሆን ማገልገል መቻል አለበት..የሰማዕትነት የምሥክርነት አይነቱ ብዙ ነው።
ፈዛዛ ደንዛዛ ሰው ለእምነቱ ግድ የለሽ አስመሳይ ሰው  የእመነት ልቡናው የሳሳ ነው።
ወገብ ልቡናን በእምነት ዝናር በጥብዓት ዝናር ታጥቆ የቅድስት ወንጌል ምሥክር መሆን ነው እንጂ በቃል ብቻ አማኝ መባል በቂ አይደለም።
በልብ አምነው በቃል ቢክዱ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስ መሆን ነው።
በልብ ክደው በቃል ቢያምኑ እንደ ይሁዳ መሆን ነው።
በልብ አምነው በቃልም መሥክረው ቢገለጹ ግን እንደ ቅዱስ መርቆሬዎስ እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ መሆን ነው።
በዚህ ዓለም የምታገኘን መከራ ሁሉ በቅዱሳን አባቶቻችን ሕይወት እና በቅዱሳት መጻሕፍት የለመድናት ናት።
ያመኑበትን ካልመሠከሩ ግን እውነተኛ አማኝ አይባሉም።
በሃይማኖታችን ምክንያት በየዕለቱ የሚያገኙን ፈተናዎች ትንንሽ መስቀሎች ናቸው።
"መስቀሉንም የማይዝ በኋላዬም የማይከተለኝ ለእኔ ሊሆን አይገባውም።"ማቴ.፲፥፴፰ እንዲል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Feb, 10:10


"ኢትዮጵያ የሰማይ ጎረቤት፣የምድር እንብርት፣የአፍሪካ ንግሥት፣የዓለም እመቤት ናት።"ሊ.ሊ.አያ.ተአ.

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Feb, 09:57


ይህ ብሌት የማዶው እና የማዶው ምደ -ጽሑፍ እንዳይገናኝ መግቻ ሲሆን የራሱ ጽሑፍም በሲራኩ እንዳይያዝ  የሚለያይ ክፍት  ቦታ ነው፡፡ በእያዳነዱ አዓምድ ካየነው ማዕዘንነትን ፈጥሮ እናገኘዋለን፡፡ ይህ ሲተረጎም ግሌት ከንባብ ጎን ከጽሑፍ  ጎን ያልተጻፈበት ቦታን ያሳየናል፡፡ይህ ያልተጻፈ ቦታ እና የተጻፈበት ቦታ ሲነጻጸሩ ዘመነ መጻሕፍትን ና  መጻሕፍት ያልነበሩበትን ዘመን ያስረዳናል፡፡ ማለትም ያልተጻፈበት የዘመነ ሕገ ልቡና ተጻፈበት ግን የዘመነ መጻሕፍት ማሳያ ነው፡፡ ያልትጻፈው በሁሉም አርዕስት ላይ ይገኛል፡፡ ከዘመነ ኦሪት የምትቀድም ሕግ ሕገ-ልቡና እንደሆነች ያሳየናል፡፡ የተጻፈው  ሁሉ ካልተጻፈው  በታች መሆኑ ሕግ ሁሉ ከልቡና ሕግ በታች ነውና በዚያውም ላይ  ሕግ የተሠራው ሰው በልቡና-ሕግ መኖር ሲቅተው ሲሆን የተጻፈ  ሕጉም ከበደል በኋላ የመጣ መሆኑን እና ሕግ የሚሰራው ለጻድቃን ያይደለ ለኀጥአን መሆኑን ያሰረዳናል፡፡ ‹‹ወነአምር ዘኒ ከመአኮ ለጻድቃን ዘይሰራዕ ሕግ ለጻድቃን ዘዕንበለ ዳዕሙ ለኀጥአን-ሕግ የሚሠራው ለኃጥአን ነው እንጂ ለጻድቃን አይደለም፡፡ ፩ጢሞ፩፥፰ እንዳለ።በዚህም ሰው ከሕግ በላይ ሆኖ ሕግን ሠርቶ ጨርሶ ያለ ሕግ መኖር የሚገባው ፍጡር መሆኑን ያሳየናል፡፡ ነቢየ እግዚአብሔር ሄኖክም ‹‹እስመ ኢተወለደ ሰብእ ለዘከመዝ በቀለም ወበማየ ሕመት ያጽንዑ ሃይማኖቶሙ እስመ ኢተፈጥረ ሰብእ ዘእነበለ ከመ መላዕክት ከመይንበሩ ጻድቃነ ወንጹሓነ-ሰው ለንዲህ ያለ ስራ አልተፈጠረም በጥቁር ቀለምና በቀይ ቀለም ጽፈው ሃይማኖታቸውን ሊያጸኑ ሰው  ለእንዲህ ያለ ሥራ አልተፈጠረም ነበርና››፡፡ሄኖክ ፲፱፥፳፬  ብሎ ከሕግ በላይ ያለሕግ መኖር  የሚገባው ፍጹም መላእክትን የመሰለ ሕያው ፍጥረት መሆኑን ያሳየናል።ስለዚህም ባልተጻፈው ቦታና በተጻፈው ቦታ ያለው ልዩነት እንደ ሕገ ልቡና ና እንደ ሕገ ኦሪት ሲሆን የመጻሕፍት መልክና አቀማመጥም ይህን መሠርት ባደረገ የተሠራ ነው፡፡ ብሌት ተባለው ንጹሕ ቦታም ትርጓሜው እንዲሁ ነው፡፡  በሌላም መልኩ የሚታየው ነገር ግን ከመነበብና ከመነገር የራቀው ብሌት ከመታወቅ ያለፈ የባረ -መጻሕፍት ምሥጢር ማሳያ ነው፡፡ መጽሐፍ ዙሪያውን የተሸፈነው ባልተጻፈ ነው፡፡ ተጽፎ ከምናውቀው ይልቅ ሳይጻፍ የቀረው ምሥጢር እንደሚበዛ  ለማጠየቅ ነው፡፡ ልክ መድኅነ ዓለም ክርስቶስ አምስት እንጀራ እና ሁለት ዓሣ አበርክቶ ለአምስት ሽህ ሰው ካጠገበ በኋላ የተረፈው አስራ ሁለት ቅርጫት ሞልቷል፡፡ ማቴ ፲፬፥፳ ይህ አምሰት እንጀራ የንባብ መጻሕፍት ምሳሌ ሲሆን የተረፈው ግን ከመታወቅ ከመነገር በላይ የሆነው የምሥጢረ መጻሕፍት ምሳሌ ነው፡፡ ማለትም ሰወቹ የበሉት ጥቂቱን  ነው፡፡ የተረፈው ግን ብዙ  ነው፡፡ የታወቀው ጥቂት  ነው ከመታወቅ በላይ የሆነው ግን ብዙ ነው፡፡ ሊቁ አባ ሕርያቆስ የእመቤታችንን ዉዳሴ ሲናገር "አኮ በአብዝኆ አላ በአውኅዶ- በማብዛት አይደለም በማሳጠር ነው እንጅ" ብሏል፡፡ ማለትም ንባቡን በማብዛት ምሥጢሩን  በማሳነስ አይደለም፡፡ ንባቡን በማሳነስ ምሥጢሩን በማብዛት ነው እንጂ ማለቱ  ነው፡፡ ስለዚህም መጻሕፍት በንባብ ጥቂቶች በምሥጢር  ግን ብዙወች ናቸው፡፡ ዓምደ መጽሐፍ ዙሪያውን በአርዕስትና በኅዳግ በግሌትና በብሌት ተከቦ በባዶነት የሚገኘው ህንን ለማስረዳት ነው፡፡ ከጽሁፍ በላይ ጽሑፍን የወለደው ቅዱስ ትውፊት ዙሪያዉን እንደከበበው እንረዳለን፡፡ይህ ከመነገርና ከመታወቅ በላይ ነው፡፡ ብሌት የዚህ ትርጉም ዋነኛ ባለቤት ነው፡፡ መጻሕፍትን ስናነብ ይህ መኖሩን  ልናዉቅ ይገባናል፡፡ በሌላም ምሥጢር ነባብ  ያረፈበት ቀለም የወደቀበት ቦታ ነባቢት ነፍስ በኢነባ ስጋ አድራ መኖሯተን ሲያስረዳን ወረቀት ቃላትን ተሸክሞ ተጽፎበት ማየታችንም ኢነባቢ ሥጋ ነባቢት ነፍስን ገንዘብ አድርጎ ለመኖሩ ማሳያ ነው፡፡ አሳብ በወረቀት ላይ መስፈሩ ነፍስ አእመሮዋን ለብዎዋን የምትስለው በነባቢት ነፍስ መሆኑን ያሳያል፡፡ ሌላም  ወረቀቱ በቃላቱ ረቂቅ እንዲባል ቃላቱም በወረቀቱ ግዙፍ እንዲባል ነፍስ በሥጋዋ ግዙፍ ብትሆንም ሥጋ  በነፍስ ደግሞ ረቂቅ መሆኑን ይገልጽልናል፡፡ ይህ በሥጋዌ እንቀፅ ሲተረጎምም በተዋሕዶ የመለኮት ገንዘብ ለሥጋ የሥጋ ገንዘብ ለመለኮት ገንዘቡ መሆኑን በመጻሕፍ እና በአሳበ መጽሐፍ እናውቃለን፡፡አራቱ ክፍሎች ሁሉ ሲተረጎሙ  መልክአ መጽሐፍ እንዲህ ሚራቀቅበትና የሚመሠጠርበት ስመ ክፍለ መጽሐፍ ነው፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Feb, 09:57


  ቅዱሳት መጻሕፍት አራት መዓዝነ መጽሐፍ ይመሠጠራሉ፦
፣አርዕሰት፣በኅዳግ፣በግሌት፣በብሌት፦
[  ] ፩.አርዕስት፦
በመጻሕፍት ግጻዌ ላይ የሚገኘው የመጀመሪያው አርዕስት ይባላል፡፡ አርዕሰት ማለት ራስ ርዕሰ መጻሐፍ የመጽሐፍ ራስ ማለት ሲሆን በላይ በኩል ያለው ህዳገ ለዕል ማለትም የላይ ህዳግ ባዶ ቦታ ርዕሰ መጽሐፍ ይባላል፡፡ በሌላም መልኩ አንቀፅ የሚነሣበት የርዕሰ አንቀጹ ርዕስ ይባላል ፡፡
ይህኛው ርዕስ እና ህዳገ ርዕስ ይለያያሉ ህዳገ-ርዕስ ክፍቱ ባዶው ቦታ የላይ መግቻ አንዳንድ ጊዜም የገጽ ማስቀመጫ ሲሆን ስመ-መጽሐፍ የሚቀመጥበት ነው፡፡
[  ] ፪.ህዳግ፦
ሕዳግ ማለት ሀደገ ተወ ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲሆን የታች መግቻ ማቆሚያ ማለት ነው፡፡ ህዳግ የርዕሰ ጉዳይ መዝያ ተብሎ ሊነገር ይችላል፡፡ይህ ህዳግ ግን ያልተጻፈበት የታች አርዕስት ባዶ ቦታው ነው፡፡
[  ] ፫.ግሌት፦
ግሌት በግራና በቀኝ በኩል የሚገኘው ከመስመር መግቻ በኋላ ያለው የጎንዮሽ ርዕስ ባዶ ቦታ ነው፡፡ይህ እንደ ላይ አርዕስት እና እንደታች ህዳግ ጽሁፍ ያላረፈበት ቦታ ግሌት ተብሎ ይጠራል፡፡
እነዚህ ሦስቱ ባንድ ላይ ሆነው  ሲታዩ አራት ማዕዘንነትን ሠርተው ይታያሉ፡፡ ከዚያም ባሻገር ረቂቅ ሀልወተ-እግዚአብሔርን  እና ምልአተ- እግዚአብሔርን ያስረዳሉ፡፡ ህዳግ ግሌት አርሥዕት እነዚህ ሁሉ ያልተጻፈበት ልዩ ቦታ ያላቸው ሆነው ካለተጻፈበት በስተላይ ሦስቱም የህዋ ገደል አላቸው ከአርዕተ በላይ ምን አለ ቢባል? ምንም።ከህዳግ በታች ምን አለ ቢባል? ምንም። ከግሌት በኋላ ምን አለ  ቢባል? ምንም የሚል ነው መልሳችን ሊሆን የሚችለው፡፡ ሆኖም ይህ ሲመሠጠር ያልተጻፈበት የምናየው ንጹህ ቦታ የምንረዳው እና በትቂቱ ለሃይማኖት ያህል የምናዉቀው የእግዚአብሔር የባህሪው መገለጫ የሆነው ጥቂቱ የሚታወቅበት የሚመረመርበት ዕውቀት ነው፡፡ ማለትም ከመጽሐፍ በላይ ባልተጻፈ ቦታነት መታየቱ ወይም መነገሩ እግዚአብሔር ከመታወቅ በላይ መሆኑን መናገር ነው፡፡ ከርዕስ በላይ የመጽሐፉ ማኅለቅት ምንም የሌለው ሆኖ እናገኘዋለን ማለትም መጽሐፉን በእጃችን ብድግ አድረገን ይዘነዋ እንበል? አሁን በዚህ ጊዜ የመጽሐፉ አርዕሠተ- አድማስ ለሚያየው ተመልካች ህዋ ወይም ገደል ሆኖ ያገኘዋል እንጂ  ሁሉ መጽሐፍ ሆኖ ያለ መጽሐፍነት ያለ ቦታ የምናገኝ አይደለም።ከጽሁፉ በላይ ያለተጻፈበት አርዕሰት እንዳለ ካርዕስቱም በላይ አካለ መጽሐፍ የሌለበት ልዩ  ዓለም እናገኛለን፡፡ ይህም ማለት የእግዚአብሔር ቅድምና እይመረመሬነት የሚታወቅበት ነው፡፡ ወደዚያ ጽሑፍም ሆነ ሃሳብን እንደማሳናሰፍርበት እግዚአብሔርም ከአሳብ ሁሉ በላይ ነው፡፡ ዳግመኛም ዓለመ-ቀለም ወይም  ቀለሙ የተጻፈበት በመሥመር የተደረደረው የዚህ ዓለም የሥነ-ፍጥረት ምሳሌ ሲሆን በአራቱም መዓዝን ከጽሑፍ ውጭ የሆነው ቦታ ግን ፍጥረትን ያሰገኘ ፈጣሬ ፍጥረታት ማለትም የፈጠረ እንጂ ያልተፈጠረ ፈጣሪ መኖሩን መናገር ነው፡፡ ወደ ላይ የሚያሳየውን አርዕስትና ከአርዕስት በላይ  ያለው ቅድምናውን እና የቅድምና ቅድምናውን ያመለክተናል፡፡ በጥቂቱ  የምናየው ያልተጻፈበት ባዶው ቦታ በቅድምና መኖሩን እና የቅድምና ምሥጢሩን በጥቂቱ ለማወቃችን ማሳያ ሲሆን ከሚታየው በላይ ያለው ባለመታየት የሚታየው ቦታ ግን እግዚአብሔር በቅድምናው እንደምን ያለ ቀዳሚ መሆኑን በድርስ ዕውቀት አለመረዳታችንን ምናገር  ነው፡፡ በታች በኩል ያለ የህዳጉ ተረጓሜውም ተመሳሳይ ነው፡፡ ማለትም መግቻው ወይም ህዳጉ እግዚአብሔር በድኅርናው ይሚታወቅበት የሚነገርበት ምሠጢር ሲሆን ከሚታየው ህዳግ በታች ያለው የማይታየው ህዳግ ግን እግዚአብሔር በድኅርናው ከመታየት ከመመርምር የራቀ መሆኑን መናገር ነው፡፡ ማለትም በድህርናው ምን ያህል ዳህራዊ እንደሆነ ደሀራዊነቱን የሚያውቀው አለመኖሩን መናግር ነው፡፡ በጎንና በጎን ያልው ግሌትም በማዕከላዊነት በምልላተ ዓለምነት ጸንቶ መኖሩን ማሳያ ነው፡፡ ማለትም ከግሌት በኋላ የማይታይ የህዋ ግሌት እናገኛለን፡፡ የሚታየው እና የሚዳሰሰው ነገር ግን ያልተጻፈበት አካለ ግሌት እግዚአብሔር በማእከላዊነቱ የሚታወቅበት እንደ  ሰው ልጅ የሃይማኖት ጽናት እንደ አእምሮ ስፋት የሚገለጽበት እና የሚታወቅበት ጥቂት ማሳያ ሲሆን፤ ከመታየት በላይ የሆነው አካለ ግሌት ግን ከመታወቅ በላይ ሆነው የማእከላዊነቱ ማሳያ ነው፡፡ ይህ በሌላ አገላለጽ አርዕስት የጽርሐ አርያም ህዳግ የመሠረተ-ምድር የማዶ ግሌትና የማዶ ግሌት የአድማስ  እና የአድማስ ምሳሌ ነው፡፡ ከአርእስት በታች ከህዳግ በላይ ከግሌት ውስጥ ያለው ዓለመ-ጽሑፍ ከጽርሐ አርያም  በታች ከመሠረተ- ምድር በላይ ከአድማስና ከአድማስ ወዲህ ያለው ዓለም ምሳሌ ነው፡፡ከአርእስት በላይ ያለው የማይታወቀው ከጽርሐ አርያም  በላይ በምልአት ያለወሰን ላለው የባሕርየ እግዚአብሔር ማሳያ ሲሆን ከአርዕስት በታች ያለው የማይታየው ከመሠረተ-ምድር በታች ያለው ያለፍጥረት  በራሱ ዓለምነት የሚኖረው የባሕርየ  እግዚአብሔር መገለጫ ነው፡፡ ከግሌት በኋላና ከግሌት በኋላ ያለው የማይታየው ከአድማስ በኋላና ከአድማስ በኋላ ላለ ባሕርየ እግዚአብሔር መግለጫ ነው፡፡ በሌላም አተረጓጒም አራት ማዕዘንነትን የሚያሳየን ሲሆን ይህም በክነፈ ኪሩቤል ተገለጾና በድርጊት ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡ ኪሩቤል ስድስት ክንፍ ያላቸው እንደመሆናቸው መጠን በሁለት ክንፋቸው ወደ ላይ ፊታቸውን ይሸፍኑበታል ፡፡ ይህ የአርዕስተ መጽሐፍ ማሳያ  ነው፡፡ በሁለት ክነፋቸው ወደ ታች እግራቸውን ይሸፍናሉ፡፡ ይህ የህዳገ መጽሐፍ ማሳያ ነው፡፡ በሁለት ክነፋቸው ወደ ጎን ና ወደ ጎን ረበው ይበራሉ፡፡ ይህ በጎንና በጎን ላለው ግሌተ መጽሐፍ ማሳያ ነው፡፡ ባጠቃላይ አርዕስት ቀዳማዊነቱን ዘለዓለማዊነቱን ወደ ላይ ቢወጡ ቢወጡ አይመረመሬነቱን የሚያሳይ ሲሆን ሕዳግም ድህርናዉን በድህርና ዘመን የሌለው መሆኑን ወደ ታች ቢወርዱ ቢወርዱ አይመረመሬነቱን የሚያሳይ ሲሆን ግሌት ማዕከላዊነቱን  ወዲህም ወዲህም ቢሉ ከመመርምር የራቀ መሆኑን የሚያመለክቱ ናቸው፡፡ ስለዚህ ከመጽሐፋችን ውስጥ ገበተን ምሥጢር ተከትለን  ከማንበባችን አስቀድሞ ይህን ልናይ እና ልናስተዉል ይገባል፡፡ ከዚህ የበለጠ መጽሐፍም ሊኖረን አይችልም ምክንያቱም ይህ ሁሉ በሁሉ የሆነውን የሁሉነ ባለቤት የሚያሳየን ስለሆነ ነው፡፡ ‹‹እስመ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘትማልም ወዮም  ወክመ ውእቱ እስከ ለዓለም-  ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና  ዛሬ እስከ ዘለዓለሙም ህያው ነው፡፡"ዕብ፲፫፥፰ እንዲል ይህ ከላይ ያየነውን የምንተረጉምበት ኃይለ-ቃል ነው፡፡ በሌላም መልኩ እሊህ አራቱ መዓዘኖች የአራቱ ወንጌላውያንን ትምህርት ያስተረጉማሉ፡፡አራቱ ወንጌላውያን በአራቱ መዓዝን ለማስተማራቸው ምሳሌ ናቸው።
[  ] ፬.ብሌት፦
ብሌት ማለት በመጻሕፍት በጥራዝ እና በጥራዝ መካከል ያለው ክፍት  ቦታ ሲሆን አንዳነድ ጊዜም በብራና አጻጻፍ ጥራዝን ከጥራዝ ለማያያዝ የውግ የስፍ ወስፌው ያለፈበት ቦታን ትቶ ከጽሑፉ ወይም ከዓምዱ እስከ ሲራኩ ያለው ክፍት ቦታ ነው፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Feb, 05:37


"ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ።"ኤፌ.፭፥፲፮
ብዙ ወገኖች ክርስቲያናዊ ድርሻን ላለመወጣት እና በክርስቲያኖች ላይ ያለውን መከራ በሀላፊነት እንዲቀል ላለመሥራት ከሚጠቅሷቸው ጥቅሶች አንዱ ይሄ ከላይ ያለው ጥቅስ ነው።
በቃ ጊዜው የሥራ ዘመን አይደለም፣መፍትሄው ዝም ማለት ነው፣መስሎ እንዳላዩ ማለፍ ነው..ወዘተ በማለት ከእውነታው እና ከሁኔታው ጋራ ሲፋቱ እና ሲጋጩ ይስተዋላል።
ሐዋርያው እንዳለው ጊዜውን መዋጀት ማለት ጊዜውን በአስመሳይነት ማለፍ ማለት አይደለም።
ወይም ዘመን የወለደውን ሹም የወደደውን ሃይማኖት በመጫን ምን ይደረግ ወቅቱ ነው እያሉ ማለፍ አይደለም።
ትናንትን ተረድቶ ዛሬ ካለው ይልቅ ነገ ቤተ ክርስቲያንን ሊገጥማት የሚችለውን መከራ ቢቻል ጨርሶ ለማስቀረት ባይቻል ለመቀነስ አስቦ አስልቶ በመሥራት ነገን መዋጀት ሲቻል ነው እንጂ ለይመሰል ነጠላ ለብሶ ብቻ በመንጦልጦል አይደለም።
ትናንት የት ነበርን?አሁን ምን ሁኔታ ላይ ነን? ነገ ምን ሊገጥመን ይችላል? ብሎ መላሽም ጠያቂም ራስን አድርጎ  ወቅቱን የሚመጥን ሥራን በመሥራት ዘመኑን መዋጀት በቀኖቹ ላይ መሠልጠን ነው።
አስመሳይነት፣መስሎ ማደር፣በሰው ደም ለመኖር መሞከር፣ሀሜተኛነት፣ዕንቅፋትነት፣ቧልተኝነት..ዘመኑን የመዋጀት ምልክቶች አይደሉም።የእምነት አልባነት የባዶነት፣መስቀልን የመግፋት ..ምልክቶች ናቸው።
ጊዜውን መዋጀት ማለት ግን፦
[  ] ሁኔታን በተረዳ አስተምህሮ።
[  ] ሁኔታን በተረዳ አገልግሎት።
[  ] ሁኔታን በተረዳ ተግባረ ክርስትና።
[  ] ሁኔታን በተረዳ አስተሳስብ።
[  ] ሁኔታን በተረዳ ዕቅድ።
[  ] ሁኔታን በተረዳ ክንውን።
[  ] ሁኔታን በተረዳ ሕይወት..ራስን ስለሌሎች ሲሉ ለሰማዕትነት አሳልፎ በመስጠት የክርስቶስን መስቀል መሸከም ሲቻል ነው።
በዘመን እየተጉላሉ፣በዘመን እየተፈናቀሉ፣በዘመን እየተቀተሉ፣በዘመን እየተናፈሉ፣..እንዳላየ እንዳልሰማ ዝም ብሎ የክርስቶስን መከራ መስቀል መግፋት ምእመናንን መርሳት የጥርጥር የክህደት የማስመሰል አካል ነው እንጂ ዘመንን መዋጀት አይደለም።
ዘመኑ ያልገባቸው አስመሳይ ዘመነኞች ከመሆን በላይ ምን የፍርሀት እና የክህደት ምልክት አለ?
በዓለት ላይ እንደወደቀው ዘር ሳያፈሩ በየጊዜው በወጣው የመከራ ፀሐይ ሁሉ እየደረቁ ከፍሬ ክብር መድረስ እንዴት ይቻላል?
ጌታችን በምሳሌው፦"ሌላውም ብዙ መሬት በሌለበት በጭንጫ ላይ ወደቀ ጥልቅ መሬትም ስላልነበረው ወዲያው በቀለ ፀሐይ በወጣ ጊዜ ግን ጠወለገ ሥርም ስላልነበረው ደረቀ።"ማቴ.፲፫፥፭ እንዳለን ሥር የሌለው ሁኖ ፈጥሮ መድረቅን እንደ ተግባር የያዘው የሰው ልቡና ነው እናስብበት።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Feb, 04:18


ሃይማኖትን በፍርሀት እኖራለሁ ማለት ከክህደት ይቆጠራል።
እግዚአብሔርን አመልካለሁ በነፍስ እጸድቃለሁ የሚል ሰው የሚፈራው ማንን ነው?
"ዝቅ ብሎ በአቴን ከፍ ብሎ አንገቴን" እቀጣለሁ በሚል ፍርሀት  ሃይማኖት አትገለጽም።
ፍርሀት ከክህደት የሚለይበት ግብር የለውም።
ጌታችን መድኅነ ዓለም ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያቱን፦"እናንተ እምነት የጎደላችሁ፥ ስለ ምን ትፈራላችሁ?" ማቴ.፰፥፳፮ እንዲል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

31 Jan, 14:39


   ከመሥራት መረዳት ይቀድማል።
ያልተረዳነውን እምነት እንኑርህ ስንለው ለተለያየ ስህተት ሊዳርገን ይችላል።
ያልገባው ግራ አጋቢ ከመሆን የገባው አስገንዛቢ መሆን ይሻላል።
[  ] ሳይረዳቸው የሚመክሩ፣
[  ] ሳይረዳቸው የሚመንኑ፣
[  ] ሳይረዳቸው የሚዘክሩ፣
[  ] ሳይረዳቸው የሚሠሩ፣
[  ] ሳይረዳቸው ባሕታዊ የሚሆኑ፣
[  ] ሳይረዳቸው የሚሰብኩ፣
[  ] ሳይረዳቸው የሚመሩ፣
[  ] ሳይረዳቸው የሚሾሙ፣...ማደናገር እንጂ መሆን አይችሉም።
በዚያውም ላይ ለተረዳው ሰው እንቅፋት ከመሆን አይዘሉም።
የምንሠራው ነገር በተቻለ መጠን ሊገባን ሊረዳን ይገባል።
የተረዳ ሰው ራሱም በጥሩ መንገድ ይሠራል ካልሆነለትም የሚሠሩትን ያበረታታል።
ቢቻል መሥራት ካልሆነ ግን ለሚሠራ እንቅፋት አለመሆን ትልቅ ቸርነት ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

31 Jan, 14:21


    ስንፍና ሰማይ ጠቀስ ደዌ ናት።
ወደዚህች ዓለም የመጣነው የሥጋና የነፍስ ትሩፋትን እንድንሠራ ነው።
የሥጋ ዓለምም ስንፍናን አይወድም።የነፍስ ዓለምም ስንፍናን አይወድም።
ሰነፍ በምድርም በሰማይም አይጠቅምም።
ስንፍና የዓመት ልብስ የዕለት ጉርስ ያሳጣል።በነፍስም ወጥተው ወርደው የሚያገኙት የትሩፋት ጸጋስ ይቅርና በአርባ በሰማንያ ቀን ያገኘናትን ልጅነት ያሳጣል።
የማይሠራ ሰነፍ ሰው የሰው እንጀራን እንዳይበላ መጽሐፍ ከልክሎታል፦"ሊሠራ የማይወድ አይብላ ብለን አዘናችሁ ነበር።"፪.ተሰ.፫፥፲ ብሎ።
ስንፍና ሀልዎተ እግዚአብሔርን ጭምር ያስረሳል።"ሰነፍ በልቡ አምላክ የለም ይላል።"መዝ.፲፫፥፩ እንዲል።
ስንፍና ትልቅ ሰማይጠቀስ ደዌ ናትና በትጋት መድኃኒት መቃወም ይገባል።
ሰነፍ ሰማዩ መና ያውርድ፣መሬቱ ውኀ ያፍልቅ ቢል አይሆንለትም።
በምኞት ደዌ ተመርዞ በስንፍና አልጋ ተኝቶ በምኞት ደዌ ተመትቶ ፍጹም መቸገሩ አይቀሬ ነው።
ማንም ሰው በተፈጥሮ የተሰጠውን ጸጋ መጠቀም ከተቻለ ትጋትን እንደ ሸማ ተግባርን እንደ ጫማ መልበስ ይችላል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

31 Jan, 12:26


የእውነተኛ ፡  የዓላማ ፡ ጉዟችን ፡ ምስክሮች ፡ ምን፡ ምን ናቸው??
የመጀመሪያው ። ምሥክራችን ፡እራሱ፡ እግዚአብሔር ፡ነው። በአርአያውና ፡ በአምሳሉ ፣ ለመፈጠራችን ፣በምድር ፡ እንሥሳትና ፡ አራዊት ፡ እፅዋትና ፡ አዝርዕት፡ ነፋሳትና፡ አብህርት  ፡በላይ ፡በሠማይ ፡ፀሐይና ፡ጨረቃ ፡ከዋክብትና ሰማያት ፡ መላእክት፡  ምስክር፡ አይሆኑንም ። አርያውንና ምሳሌውን ፡ የሠጠን  ፡ሥላሴ ፡ ነው ፡ ምሥክራችን ።

《》ለመፈጠራችንም ፡ ምስክሩ ፡እርሱ ፡ነው ።
ሰውን ፡እንደአርያችንና፡ እንደምሳሌያችን፡ እንፍጠር፡ የሚለው ፡አምላካዊ፡ ምሥክርነት ፡ዘመን፡ የማይሽረው፡ ሕያው ፡ምሥክር፡ ነው ።

《》ለመኖራችንም። ለልጅነታችንም ።ምስክሩ፣ እርሱ፡ ነው በአብ ፥ በወልድ ፥ በመንፈስ ቅዱስ ፥ ስም ፡አጥምቋቸው፡ ያለው፡ አምላካዊ ፡ምስክርነት፡ በሽምግልና፡ የማይለወጥ፡ መዋኤ ፡ ዘመን ፡ ነው።
መጻሕፍት ለመጻፋቸው ለስነፍጥረት አኖኗርና ፍጻሜ ዘመናችን፡ እውነተኛው ምስክር እርሱ ነው።

《》የእውነተኛ ጉዟችን ሁለተኛው ምስክር ሥነ ፡ ፍጥረታት፡ ናቸው።
ሥነ ፍጥረት በሥርዓታቸው መኖር ካልችሉ ዓለም ከእነጓዙ  መኖር አይችልም ። በጋና ክረምት ቀንና ሌሊት እሳትና ነፋስ ሠማይና ምድር ለሰው ለጆች ምቹ የሆኑት በሥርዓት ስለሚኖሩ ነው።
ሥርዓት ከሌለህ እንኳን ለሰው ለራስህ ፈተና ነህ።
ሥራህን በሥነ ፍጥረት ምስክርነት ካላረጋገጥህ ሦሥተኛውን የዓለም ጦርነት ከራስህ ጋርና ከሥነ ፍጥረት ጋር ለማድረግ ከጨለማው ገዥ ጋር ዝግጅት እየአደረግህ ነው ማለት ነው።
《》ሦስተኛው ደግሞ በመጻሐፍትና በአበው የሕይወት ምሥክርነት ይረጋገጣል ።
እንዲህ ከሆነ የተንኮለኞችን ሴራ ትረዳለህ ። የነርሱን ሴራ ከተረዳህ ፤ ከራስህ ጋር አንድ ትሆናለህ። ከራስህ ጋር አንድ ከሆንህ፤ ኦርቶዶክሳዊ አንድነት ይኖርሀል።
ኦርቶዶክሳዊ አንድነት ካለህ፣ የሥላሴ ማደሪያ ትሆናለህ። የሥላሴ ማደሪያ፡ ከሆንህ  ፡ሁሉን የሚውርስ ልጁ ትሆናለህ።
ሁሉን ወራሽ ከሆንህ ኦርቶዶክሳዊ ፍቅር ይኖርሀል ኦርቶዶክሳዊ ፍቅር ካለህ በቅን ልቡና በትሑት ሰብእና ሆነህ ታገለግላለህ በፍቅር ካገለገልህ ከሠማይ በታች ያለህ በጎ ነገር አንተ ነህ መሬትን አርሰህ ካልዘራሀት እሦህ ይሠለጠንባታል ፍሬ አልባዎች የሸፍኗታል ። እንስሳትን ካላሰማራህባት ፣ አራዊት ይነግሡባታል እንሥሳቱም ቢኖሩ እንኳን የአራዊት ምግም ይሆናሉ። ኑሯቸውም የሰቀቀን ይሆናል ። ምድራችን ጥሩ ነገርን ያለድካም አታፈራም በጎ ነገሮች ሁሉ የድካም ውጤቶች ሲሆኑ ክፉ ነገሮም የስንፋና ፍሬዎች ናቸው። በዚህ ዓለም ካንበሳ ጋር ስትኖር ስትኖር እላም አትሁን ይሰብሩሀል አንበሳ ከሆንህ አንበሳውን አንበሳ ያከብረዋል እንጅ አያሳድደውም ከነብሮች ፍየል ከተኩላዎች ጋር በግ  ከእባቡች ጋር እርግብ ሆነህ አትገኝ
    ሁሌም ከችግርህ በላይ መብረር አለብህ
            ሠናይ አስረሴ

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

31 Jan, 10:31


           የፈረስ በዓል።
የፈረስ በዓል መሠረታዊ መነሻው ከፈረሰኛው ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋራ ተያይዞ የሚታሰብ በዓል ነው።
የፈረሰኛ ማኅበርተኞችም የሚዘክሩት የሚጠጡት በቅዱስ ጊዮርጊስ የበዓል መታሰቢያ ቀን ነው።
ይሄም ማለት በ፳፫ ቀን እና ከዓመት አንድ ጊዜ በጥር ፲፰ም ያከብሩታል።
ሃይማኖተኛው ኃያሉ ሰማዕት የጀግኖች የፈረሰኞች ሁሉ የጽንዓት የእምነት የዓርበኝነት ምልክት ነው።
ይሄንን በዓል የፈጠረችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት።
ወዲህም የሰማዕቱን የቅዱስ ጊዮርጊስን ሕይወት ልጆቿ እንዲይዙ፣ወዲህም የሀገር ባለውለታ ሁነው እንዲሠሩ፣ወዲህም ምግባር ትሩፋትን እንዲለማመዱ ነው።
ይሄንን ቅዱስ ዕሴት በትክክል ከዓውዱ ሳናወጣ ከተጠቀምንበት ማንንም ማስተሳሰር የሚችል  ለቤተ ክርስቲያን እና ለሀገር የሚጠቅም ቅዱስ በዓል ነው።
ነገር ግን በዓሉ በትክክለኛው ሥሪያዊ ዓውዱ እንዳይታሰብ ብዙ የፖለቲካ ዲሪቶ እየተጨመረበት ከሆነ ግን የዕንፋሎት አይነት ነው።
አሁን አሁን እንደዚህ ያሉ የክርስትና ባህሎችን እና በዓላቶችን ሥሁት ፖለቲካ እየቀማ ከእውነታ መነሥመራቸው እያፋታቸው ይገኛል።
ባሉበት እንዳለ በሥሪታቸው መከበር መዘከር እየቻሉ ከታሪካቸው የተፋቱ ሊበራል በዓላት እንዲሆኑ እየተሠራባቸው ነው።
ለራሱ መልካም ዕሴት ፈጠራ የማይችለው የሀገራችን ሥሁት ከፋፋይ ፖለቲካ ቤተ ክርስቲያን የሠራችውን ቅዱስ ዕሴት እየተከታተለ መዋጥ እንደ ተቀዳሚ ሥራው ነው።
ልብ ብለን እንመልከት፦
[  ] የፈረሰኞች በዓል ከጥንት ጀምሮ ሥዕላቸው ተሥሎ ኃያልነታቸው እምነታቸው እየተነገረ የሚታሰብላቸውን አሁን አሁን  አንድ ዓይና ብቻ እያደረጉት ነው።
ለሀገርም ለሃይማኖትም አበርክቶት የነበረውን ቅዱስ በዓል በገንጣይ አስገንጣይ ፖለቲካ ብቻ ሲተረጉሙት አንድ ዓይና በዓል እንዲሆን ያደርገዋል።
ቢያንስ ቤተ ክርስቲያን የታሪኩ ባለቤት መሆኗን እንኳን ለመናገር እስከ ማፈረሰ የተደረሰበትን ሁኔታ ለተገነዘበ እጅግ ማዘኑ አይቀሬ ነው።
ደግሞም ለዘመናት በትክክለኛ ታሪክ ጸንቶ የኖረው ዕሤት በሀገራችን ገልበጥባጣ ፖለቲካ መርህ ውስጥ ሲከቱት  በተቀያያሪ ርዕዮት ምክንያት መማሰኑ አይቀሬ ነው።
ዛሬም ለአስተዋይ እና መዛኝ ልቡና የታሪክ ደምግ ግባቱን  እያጣ እንዳለ መስተዋል ይቻላል።
በየጊዜው የምናከብራቸው  በዓላት የትምህርት እና የታሪክ ውጤቶች ናቸው።
የሚያከብራቸው ሁሉ በትምህርታቸው እና በታሪካቸው እየተሳበ ነው።
ታሪክ፣ዕሴት፣ምንጭ፣ ትምህርት የለሽ የገረጣ ዕሴት ግን ቅዱስ ባህልን አያስቀጥልም፣ቅዱስ ታሪክን አይወልድም።
የሀገራችን ማኅበራዊ ህልውናው  ተቀድሶ ለሰው እንዲጠቅም ሁኖ የኖረው መነሻ እውነታን መሠረት ያደረገ ስለሆነ ነበር።
የእውነት ተቃራኒው ለጊዜያዊ መሳ ሰው መሳቢያ ብቻ ታስቦ የሚሠራው የሥሁት ፖለቲካ ባህል እና በዓል ግን  ትክክለኛ የታሪክ መነሻ የሌለው ድክርት ዲሪቶ ነው።
የበዓሉ አከባብርን ከነ ታሪኩ መካበር ያማረ የተወደደ ነገር ነው።
የበዓሉን ታሪክ ነጥሎ ገንጥሎ ትቶ አከብራለሁ ማለት ግን "ወፍ መንዳት ጉም ማፈስ"ነው።
ብሂሉስ፦"ሰይፉን ወደ አፎቱ ልጁን ወደ እናቱ" አይደል?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

31 Jan, 09:12


"ከሥጋ ቤት አጠገብ ያሉ ውሾች በሩ ካልተዘጋ ዘወር አይሉም።"
ከክፉ ግብር አጠገብ ያለ ሰይጣንም የኃጢአት በሩ ካልተዘጋ በስተቀር ዘወር ማለት አይችልም።
መንፈስ ቅዱስ ሲያድር ልቡናን ወደ ቅድስና ወደ ቸርነት እንደሚመራው ሁሉ በአንጻሩ ርኩስ መንፈስም በሰው ሲያድር ከቀደመው የበለጠ ይከፋ ዘንድ ሰውየውን በክፋት ያተጋዋል ያዘጋጀዋል።
ከሥጋ ቤት በር ያለ ውሻ የሚርቀው በሩ ሲዘጋበት ነው።
ከሥጋዊ ግብር በር ያለ ሰይጣንም ዘወር የሚለው  የክፉ ህሊናት በሮችን ስንዘጋቸው ብቻ ነው።
በሩን ሳይዘጉ ሥጋውን እያሳዩ ከውሻ ጠባይዕ ሰላም መሆን አይቻልም።
ከሁሉም ትሩፋት በላይ ቤተ ልቡናን ዘግቶ መጠበቅ ይበልጣል።
ከሁሉም ኃጢአት በላይ ቤተ ልቡናን ከፍቶ የሁሉ መመላለሻ ማድረግ ይከፋል።
የድቀት በሮች የሚከፈቱት ደግሞ ከንዝህላልነት የተነሣ ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

31 Jan, 08:59


"በሁሉም ስለ ስሜ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።"ማቴ.፲፥፳፪
የወንጌል ንባብ በአካላቸው የተፈጸመባቸው ቅዱሳን ሰማዕታት ናቸው።
እንዲህ ወድቀው ወድቀው መራራ ሞትን የተቀበሉ አባቶች የእውነት ትርጉም ናቸው።
የተጻፈውን በአካላቸው የገለጡ ለእውነት እና ለዘለዓለም ሕይወት የምድራዊነት ሕይወትን የለወጡ ናቸው።
በዓላውያን ነገሥታት በዓላውያን ሹማምንት ምክንያት የመጣባቸውን መከራ እንደ ሽልማት ቆጠሩት።
ዘመን የወለደውን ሹም የወደደውን ሳይሉ ለቅድስት ቃለ ወንጌል ታምነው በየ ቦታው ወድቀው ወድቀው ይታያሉ።
ግን እንደ ንጹሕ ስንዴ ለእግዚአብሔር  መባዕ ሁነው የቀረቡ ድንቅ ስጦታዎች ናቸው።
ሰው አፍአዊ ገንዘቡን ምጽዋት አድርጎ ቢሰጥ አይደነቅም።
ሰማዕታት ግን አንዲት ሕይወታቸውን መባዕ አድገው ነው ያቀረቧት።
ቤተ ክርስቲያን በብርሃነ ሃይማኖት ጸንታ የበቀለችው በእነዚህ የትሩፋት ደም ላይ ስለምትመላለስ ነው።
የክርስቶስ መስቀሉን በአንገታቸው ብቻ ሳይሆን በውድ አንዲት ሕይወታቸው ላይ አሥረው ተባረኩበት።
አንዱ ክርስቶስ ደሙን አፍስሶ ሲዋሐዳቸው አይተው በአንዲት ሕይወታቸው ደማቸውን አፍስሰው ተዋሐዱት።
የሰማዕታት ሞታቸው መራራ ቢሆንም ከሞት በኋላ የሚገኘው ሕይወቱ ግን ጣፋጭ ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

07 Jan, 15:30


ባህል እና በዓል፦
[፦ቅዱሳን በዓላት የምልኮት መፈጸሚያዎች ናቸው።
[፦አንድ ሰው በዓል እያከበረ ነው ማለት አምልኮቱን በትክክል እየኖረው ነው ማለት ነው።
[፦በዓል ሁልጊዜ መላልሰን የምንኖረው ከሆነ የሕይወት ባህል የአምልኮት ብርሃን ይሆናል።
[፦ባህል የንጹሕ ትምህርት መገጫ ነጸብራቅ ነው።
[፦በትክክለኛ ነገረ ሃይማኖት የተገነባው እውነተኛው አምልኮት አካል ገዝቶ የሚታየው በበሀል በኩል ነው።
[፦ስለዚህ የበዓላት ባህልን መጠበቅ ሃይማኖትን መጠበቅ ነወ።
[፦ከዚህ ባፈነገጠ አምልኮታዊ ቅዱስ ባህልን የሥሁት ርዕዮተ ዓለም ልብስ ሲያለብሱት ቅድስናውን የለቀቀ ድርት ትርክት ይሆናል።
[፦ለዚህ ዲሪቶ ትርክት ትርክት ደግሞ ለጥፋተ-ባህል የሚሠሩ የተለያዩ የጥፋት ተቋማት ዋነኞች ናቸው።
[፦ስለሆነም ዕቅበተ እምነት እንደሚያስፈልግ ሁሉ ዕቅበተ ባህልም ያስፈልጋል።
[፦ባዕድ ነገርና ባዕድ የባህል ወረራን ስናይ የጥፋት ቫይረሱ እንዳይለክፈን መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
[፦በየቤታችን በዓላትን ስናከብር በድፍረት ወይም በስህተት ወይም በሴራ ወይም በሥሁት ሥርዓት ወይም በስንፍናችን ምክንያት እውነተኛ አምልኮቱን ወደ ማይገልጽ አከባብር እንዳንሄድ መጠንቀቅ ያስፈልገናል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

07 Jan, 15:22


ቅዱስ ሊላበላ
[  ] ቅዱስ ላሊበላ ፲፩ን ቤተ መቅደስ ሠርቶ ምእመናን ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ሲጓዙ በግብጽ በረሀ፣በስዊዝ ካናል እና በየመንገዱ ወድቀው ወድቀው ይቀሩ የነበሩትን ማዳን ችሏል።
[  ] ዳግማዊ ኢየሩሳሌምን በዚሁ በሀገራችን በደብረ ሮሐ በመሥራቱ ዕረፍተ ሥጋን ዕረፍተ ነፍስን አስገኝቷል።
[  ] ይህ ገዳማዊ ጉዞ ከንግሥተ ሳባ ጀምሮ በንጉሥ ባዚን እና በጃንደረባው ተገልጾ ነበር።
[  ] አሁንም ይሄ ገዳማዊ ጉዞ የክርስትናችን መገለጫ ሁኖ እየተፈጸመ ይገኛል።
[  ] ነገር ግን የቱሪዝም መልክ፣የቅርሳቅርስ መል፣የገንዘብ መሰብሰቢያ ብቻ ዓላማን እየያዘ መንፈሳዊ ሕያውነቱን እንዳያጣ ጥብቅ ጥበቃ ይጠይቃል።
[  ] አሁን አሁን የምንታዘባቸው፦ በዓላት ዋና ዓላማቸውን እየለቀቁ የሥሁት ርዕዮተ ዓለም ማስተላለፊያና የገንዘብ መለመኛ ብቻ እየሆኑ እየመጡ ነው።
[  ] ዛሬ በየዋላችሁበት ቦታ የማይፈለግ ምን አዲስ ለውጥ አያችሁ?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

07 Jan, 07:38


           በዓለ ጌና(የገና ባህል)
የገና በዓል እና ባህል በሀገራችን እጅግ የተከበረ ቅዱስ በዓል ነው።ትቂት ስለ ገና ባህል እንመልከት፦
[  ] ፩.ገን፣ገነት፡- ማለት ተክል የተክል የፍሬ ቦታ (ገነት)ማለት ነው(ቃሉ የዕብራይስጥ ነው) በዚህ ትርጉም በዓለ ጌና ማለት በገነት የተመሰለችው የእመቤታችን እና በፍሬ የተመሰለው የጌታ በዓል ማለት ነው።እመቤታችንን በገነት ተክል ጌታን በገነት ፍሬ መስሎ መናገር በመጻሕፍት ዘንድ የተለመደ  ነውና።
[  ] ፪.በዓለ ጌና ማለት፡-የእመቤቲቱ በዓል ማለት ነው በዳውሮኛ ልሳን እመቤታንን የሚገልጽ ቃል ነው።በዳውሮ ልሳን እመቤታችን ለማለት ጌና በማለት ይጠራል።
[  ] ፫.በዓለ ጌና ማለት ፡-በለ አምኃ ፣በዓለ አምልኮ ማለት ነው። ከሰብአ ሰገል ጋር ባለው ታሪክ መሠረት ሦስቱ ነገሥታት ወርቅ፣ዕጣን እና ከርቤ ለክርስቶስ ከመገበራቸው ጋራ የተዛመደ ነው።
[  ] ፬.በዐለ ገንህ፡-ሁሉ ወደ እርሱ የሚጮህለት፣ሁሉ  የሚገዛለት የጌታ በዓል ማለት።
በበዓሉ ዕለትም ንጉሥ ሳይቀር ከዙፋኑ ወርዶ የሚጫወትበት በዓል ማለት ነው።(በገና ጫወታ አይቆጡም ጌታ)የሚባለው ሁሉ እኩል በትህትና ስሊሚጫወቱ ነው።
       የገና ጫወታ እና አጀማምሩ በትውፊት፦
[  ] ፩.የገና ጭወት አጀማምሩ መልአክ ለኖሎት የልደትን ብሥራት ሲነግራቸው በደስታ ወደ ቤተ ልሔም ሲሄዱ ኳስ ኳስ የመሰለ የብርሃን ጥንግ ያገኙ ነበር።
ያንን ከደስታቸው ብዛት የተነሣ እየሞጩ እየቀሉ ወደ ቤተ ልሔም ሂደዋል።
[  ] ፪.ከሄሮድስ ሠራዊት አንዱ እሩህ የሚባለው ሰው ተሠውሮ መዳረሻቸውን ለማወቅና ጌታቸውን ንጉሣቸውን ለመግደል ለሥለላ መጥቶ ነበር።
በዚህ ምክንያት ባዕድ ሲገባባቸው ይመራቸው የነበረው ብርሃን ሲሠወራቸው ተፈላልገው ለይተው ገርፈውታል በዚያ ልማድ የዕሩህ ጭዎት ተጀምሯል።
[  ] ፫.የአዳምን ነፍስ እስከ ክርስቶስ ቀዳማዊ ምጽአት ድረስ አጋንንት አበድነው በመንጸፈ ደይን ጥለው በእግራቸው ጠቅጥቀው መከራ አጽንተውባት ነበር።
በዚያ ምሳሌ ዛሬም ከወዲያ ወዲህ እሩር በመጫወት ይገልጹታል።
[  ] ፬.መላእክት ሰይፈ እሳት በትረ እሳት ይዘው ለልደት ፳፬ ቀን ሲቀር ጀምረው ዓውደ ቤተ ልሔምን ሲጠብቁ ያሳዩት የነበረው ግብር ነው።
በዚህ ጊዜ ዲያብሎስ ወደ ቤተ ልሔም ሲቀርብ ቅዱሳን መላእክት በሀጸ እሳት በበትረ እሳት እየሞጩ እየቀሉ አባረውታልና በዚያ ምሳሌ የገና ጫወታ ይካሄዳል።
[  ] ፭.ኖሎት ከብት እየጠበቁ እሩር ከሚበትጫወቱ ቦታ መላእክት  ዮም ተወልደ ብለዋቸዋልና በዚያ ትውፊት እስከ ዛሬ ድረስ የገና ጭዎት የተወቀ በዓል ነው።
፮.ዕሩር የአዳም ነፍስ ምሳሌ ናት።ያሸነፉ ገነኞች እየዘመሩ ወደ መንደራቸው ይዘዋት ይሄዳሉ።የመንደሩ ሰውም ድግስ ደግሶ እልል እያለ ይቀበላቸዋለል።
ይሄውም የጠፋውን በግ አዳምን ጌታችን ከዲያብሎስ ቀምቶ በሄደ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት እየዘመሩ የቀብለውታልና በዚያ ምሳሌ።
የገና ጭወት ንጉሥ ከነ ሠራዊቱ፣ምስለኔ ከነ መኳንንቱ፣ዓለቃ ከነ ካህናቱ የሚጫወትበት በዓል ነው።
ምክንያቱም በንጉሥ ክርስቶስ ልደት፡-ሰማያውያን መላእክት.ምድራውያን ኖሎት፣ሦስቱ ነገሥታት አንድ ሁነው ተባብረው ያከበሩት በዓል ስለሆነ በመካከል ሁሉም ክብሩን ለቆ ዝቅ ብሎ በገናው ቦታ በመገኘት ትህትናውን ይገልጻል።
ዕለቱ ዕለተ ምርያ፣ዕለተ ሣህል፣ዕለተ ምህረት፣ዕለተ ድኅነት፣ዕለተ ፍጻሜ ተስፋ፣ዕለተ ትህትና ስለሆነች ቁጣ ጠብ የሌለው በዓል ነው።በበዓሉ ጌታችን፣እመቤታችን፣ዮሴፍ ሰሎሜ፣መላእክት፣ኖሎት፣ሰብአ ሰገል ይታሰቡበታል።የነገሥታት ጫወታ የሆነው ለዚህ ነው፡፡
                    ከና ጫዎታ መልስ፦
[  ] ፩.ገናውን ሰዎች ተጫውተው ጨርሰው ወደ መንደር ሲደርሱ ሰው ሁሉ በደስታ በድግስ ይቀበላቸዋል።ይሄውም የሚጠተ ሰብአ ሰገል መገለጫ ነው።
ሰብአ ሠገል ሰግደው ሲመለሱ ሰው ሁሉ በእልልታ በደስታ ስለተቀበላቸው ነው።
[  ] ፪.ሚጠተ ኖሎት ነው።ኖሎት እነሆ እውነትም ተወልዷል በጎል ተጥሎ በጨርቅ ተጠቅልሎ በገግዕዘ ሕፃናት ሳያለቅስ ሲያነጥስ አየነው ሰማነው እያሉ በደስታ ለመመለሳቸው ምሳሌ ነው።
፫.አምላካችን ሰው ሁኖ አዳምን ከጨለማ ወደ ብርሃን ከሞት ወደ ሕይወት በመለሰው ጊዜ መላእክት ደስ እያላቸው ስለተቀበሉት ነው።
[  ] ፬.በነጋው ወተት ያለው ሁሉ ዱቄት እና ወተት ሜዳ ከትልቅ ዛፍ ሥር ከብቶች እና እረኞች ባሉበት የወተት ገንፎ ተዘጋጅቶ የተገኘው ሁሉ ይመገባል።
ምክንያቱም እመቤታችን ለመጠየቅ ኖሎት ከላሞቻቸው ወተት፣ ከስንቃቸው ዱቄት አምጥተው መግበው፣ተመግበው ስለነበር በዚያ ልማድ ነው፡፡ዛሬም በዚያ ልማድ አንዲት ሴት ስትወልድ ቀድሚያ ወተትና ገንፎ የሚያቀርቡላት ለዚያ መሠረት ነው።
               የገና ስጦታ፦
፩.የገና ሥጦታ (ጋዳ) ይባላል፡-ሦስቱ ነገሥታት ወርቅ፣ዕጣን፣ከርቤ ያበረከቱለትን መሠረት አድርጎ ያንን በማሰብ የሚተገበር ነው።
፪.ይልቁንም የሀገራችን ቀደም ብላ ንግሥተ ሳባ ለንጉሥ ሰሎሞን፤ንጉሥ ባዚን እና ሊቀ ካህናት ዮአኪን ለጌታችን  ያቀረቡትን አምኃ። የሚያትት ነው
፫.ኖሎት ወተት እና ዱቄት ለእመቤታችን አቅርበውላት ስለነበር  በዚያ ምሳሌ ነው።
፬.መላእክት የምስጋና ግብር ለጌታችው አቅርበው ነበር በዚያ  አርአያ የሚሆን ነው።
[  ] ፭. እመቤታችን ሰብአ ሰገል ስንቅ ቢያልቅባቸው"ወአስነቀቶሙ ህብስተ ሰገም-የገብስ እንጎቻ ሰጠቻቸው"ይላል እና በዚያ አርአያ ነው ነው የገና ሥጦታ የሚበረከተው።
፮.ራሱ ቃል በሥጋ ለሰው ልጅ መሰጠቱን ለማሰብ ጭምር ነው የምናበረክተው፡፡ይህም አብ አንድያ ልጁን ልጁን ለሕማም ለሞት አሳልፎ ስለሰጠልን ያንን በማሰብ የሚከናዎን ነው።..
[  ] በዓላትን ስናከብር ከእነ ዕሤቱ፣ከነ ታሪኩ፣ከነ ምሥጢሩ፣ከነ ክብሩ ሊሆን ይገባል።ባዕድ ከሆኑ የባህል ከረራዎች ራሳችንን እንጠብቅ።ይህ ባህል ሕይወታችን እንጂ  ምናብ አይደለም።
አንድ ሃይማኖት ሲኖሩት ባህል ለትውልድ ሲያቀብሉት ትዉፊት ይባላል፡፡
ባህል እና ትውፊት የሌለው ሃይማኖት ወደ ሕይወት ዘልቆ መግባት ያልቻለ ትምህርት ነው።
ባህል የማይጨበጥ ቅርስ አይደለም የዕለት ከዕለት ሕይወት ነው እንጂ፡፡
ባህል ትናንትን ለዘሬ ዛሬን ለትናንት የሚያቀብል የሕይወት መምህር ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

06 Jan, 08:21


ተወልደ በአምሳሊከ ከመ ይለድከ በአምሳሊሁ
አረ መን
በማይመስልህ ልደት ይወልድህ ዘንድ የማይመስለውን ልደት ተወለደ

፩ , ረቂቅ ነው በግዘፈ አካል ተወለደ ።
አብ ዘኢይትረከብ ወልድ ዘኢይትረከብ ወመንፈስ ቅዱስ ዘኢይትረከብ
አብ የማይመረመር ረቂቅ ነው ወልድ የማይመረመር ረቂቅ ነው መንፈስቅዱስ የማይመረመር ረቂቅ ነው ሃይ አበ ፳፰÷፴፱

፪, ምሉዕ ነው በውሱን ሥጋ ተወለደ ።
እግዚአብሔር አብ ዘላዕለ ኵሉ ወውስተ ኵሉ
እግዚአብሔር ወልድ ዘላዕለ ኵሉ ወውስተ ኵሉ
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ አሓዱ ዘሠረፀ እምአብ ውእቱ ወኃቤ ሕይወት ዘላዕለ ኵሉ ወውስተ ኵሉ

ትርጕም፦ እግዚአብሔር አብ በሁሉ ላይ ነው በሁሉም በምልዐት ያለ ነው
እግዚአብሔር ወልድ በሁሉ ላይ ያለ ነው በሁሉም በምልዐት ያለ ነው
እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ከአብ የተገኘ ሕይወትን የሚያድል በሁሉ ላይ ያለ ነው በሁሉም በምልዐት ያለ ነው ሃይ አበ ፲፱÷፬

፫, ቀዳማዊ በደኃራዊ ሥጋ ተወለደ ።
ውእቱ ቀዳማዊ ዘአልቦቱ ጥንት ወይእዜኒ ኮነ ውስተ ኍልቖ ዘመን

ትርጕም፦ እርሱ ጥንት የሌለው ቀዳማዊ ነው
ዛሬ ግን ዘመን ተቆጠረለት ሃይ አበ ፴፭÷፲፮

ውእቱ እምቅድመ ኵሎሙ ፍጡራን ቀዳም እምቀዳማዊ
ትርጕም፦ እርሱ ከፍጡራን ሁሉ በፊት የነበረ ከቀዳማዊ አብ የተገኘ ቀዳማዊ ነው
ሃይ አበ ፲፫÷፳፩
፬, ፈጣሪ ግን ፍጡር ተባለ
እስመ ክርስቶስ ኢፍጡር ወፍጡር ኀብሩ በ፩ዱ ህላዌ ወአካል ኅቡረ ንብል በእንቲአሁ ኢፍጡር እስመ ውእቱ ቀዳማዊ እምቅድመ ኵሉ ዓለም ወእስከ ለዓለም ወውእቱ ፈጣሬ ኵሉ ዘሀሎ
ወዘሰ ንቤ ፍጡር በእንተ ዘተሳተፈ ሥጋ ድካምነ በእንተ ሥርዐት ዘገብሮ በእንቲአነ

ትርጕም፦ ክርስቶስ ማለት ፈጣሪና ፍጡር አንድ አካል አንድ ባህርይ በመሆን አንድ ሆነ ማለት ነው ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ለዘለዓለም የሚኖር ያለውን ሁሉ የፈጠረ እርሱ ነውና ስለ እርሱ ስንናገር ያልተፈጠረ (ፈጣሪ) እንላለን ፍጡር ነው ያልነውም ስለ እኛ ባደረገው ተዋሕዶ ደካማ ባህርያችንን ስለ ተዋሐደ ነው ሃይ አበ ፴፭ ÷ ፪~፬

ወጥበብኒ እንተ ትትወለድ እምእግዚአብሔር በእንተ ምንት ትትፈጠር በእንተ ምክንያተ ድኅነቶሙ ለሰብእ ባሕቱ ተፈጥረት በልብሰተ ሥጋ ወአኮ ዘትትፈጠር ኵሎ አሚረ አላ ተፈጥረት ጥንተ ለፍኖተ እግዚአብሔር እንተ ለሊሁ የሐውራ ወታበጽሖ ለዘየሐውር ዲቤሃ

ትርጕም፦ ከእግዚአብሔር አብ የተገኘች ጥበብ ስለምን ትፈጠራለች ?ግን ሰውን ስለማዳን ሥጋን በመልበስ ተፈጠረች ምን ጊዜም የምትፈጠር አደለችም እርሱ ራሱ ለሚሄድባት ለእግዚአብሔር መንገድ ጥንት ሆኖ ተፈጠረች እንጂ
ሃይ አበ ፸፮ ÷ ፰

፭, ሕማም ሞት የለበትም ሕማም ሞት የሚስማማውን ሥጋ ተዋሐደ ።

አንተ ዘኢተሐምም በመለኮት ወአንተ ሐማሚ በሥጋ አንተ ዘኢትመውት ዘከመ ዕሪናከ ምስለ አብ ወአንተ መዋቲ ዘከመ ዕሪናከ ምስሌነ

ትርጕም ፦ በመለኮት ሕማም ሞት የሌለብህ አንተ ነህ በሥጋ መከራ የተቀበልክ አንተ ነህ ከአብ ጋራ አንድ እንደመሆንህ ሞት የሌለብህ አንተ ነህ ከእኛ ጋራ አንድ እንደመሆንህ በፈቃድህ የሞትህ አንተ ነህ
ሃይ አበ ፵፰ ÷ ፲፪

እኛ
፩, ግዙፋን ስንሆን በርቀት ተወለድን ።
ወካዕበ ነአምን በአሓቲ ጥምቀት ዳግም ልደት ዘእመንፈስ ቅዱስ ዘይሬስዮ ለሰብእ ሐዲሰ ልደተ ዘከሠተ ለነ መድኃኒነ ሶበ ኮነ ሰብአ ወአስተርአየ ውስተ ዓለም በፈለገ ዮርዳኖስ

ትርጕም ፦ ዳግመኛም ከመንፈስ ቅዱስ በተገኘች ዳግም ልደት በምትሆን በአንዲት ጥምቀት እናምናለን ሰውን በልደት አዲስ የማያደርገውን መድኃኒታችን ሰው ሆኖ በዚህ ዓለም በታየ ጊዜ በዮርዳኖስ ወንዝ የገለጠልን ሃይ አበ ፳፰ ÷ ፳፫

፪, ውሡን ነበርን መላን
እንዘ ውእቱ ውስተ ኅፅነ አቡሁ ተጸውረ በከርሰ ድንግል ወተወልደ እምኔሃ እንዘ ውእቱ ውስተ ኅፅነ እሙ ያንሶሱ በክነፈ ነፋስ ወይሰግዱ ሎቱ መላዕክት

ትርጕም፦ እርሱ በአባቱ ኅሊና ሳለ በድንግል ማኅጸን ተወሠነ ከእርሷም ተወለደ እርሱ በእናቱ እቅፍ ሳለ በነፋስ ክንፍ ይመላለስ ነበር መላዕክትም ይሰግዱለት ነበር ሃይ አበ ፵፰ ÷ ፪

፫, ደኃራውያን ነበርን ቀዳማውያን ሆን
ለምንት ኢይቤ እምህላዌነ ነስአ አላ ይቤ ነስኦ ለህላዌነ ከመ ብእሲ ዘተኀጥአ ፍቅሩ ወሖረ ለሐሲሶቱ እስከ ረከቦ ወነስኦ ከመዝ ህላዌ ዚአነ ተኀጥአት እምእግዚአብሔር ወርኅቀት እምኔሁ ጥቀ ወሮፀ ድኅሬሃ እስከ ረከባ ወነስኣ ወይእቲኒ ተወክፈቶ ወክሡት ግብሩ እስመ ውእቱ ገብረ ዘንተ በአፍቅሮቱ ኪያነ

ትርጕም፦ባህርያችን ተዋሕዷል እንጅ ከባህርያችን ከፍሎተዋሐደ ለምን አላለም ወዳጁ እንደ ኮበለለ እስኪያገኘውም ድረስ እንደሄደና እንደ አገኘው ሰው የእኛ ባህርይ እንደዚሁ ከእግዚአብሔር ተለይታ ነበርና ከእርሱም ፈጽማ ርቃ ነበርና ሥጋ በመሆን ገንዘብ እስኪያደርጋት ደርሶ ፈጥኖ ፈለጋት እርሷም ተዋሐደችው ይህንንም ተዋሕዶእኛን በመውደድ እንዳደረገው የታወቀ ነው ሃይ አበ ፷፫ ÷ ፭

፬, ፍጡር ነበርን ፈጣሪ ሆንን።
ዘከመ ፈቀደ ፈጠረ ሰብአ እምድንግል ወለብሰ ወተዋሐደ ምስሌሁ ወወጽአ ዮም ወኢያስተተ ህጸጸ ህላዌነወኢረሰየ ሎቱ ህጸተ ሶበ ለብሰ አባሎ ወዳእሙ ፍጡር ረብሀ ስብሐተ ዓቢየ ሶበ ኮነ ልብሶ ለፈጣሪ

ትርጕም፦ እነደ ወደደ ከድንግል ሥጋን ነፍስን ፈጥሮ ተዋሐደ እርሱንም ተዋሕዶ ዛሬ ተወለደ ህጸጽ ያለበት ነው ብሎ ባህርያችንን አልተወውም ሥጋን በተዋሐደ ጊዜ ቃል ከምልዐቱ አልተወሠነም ሥጋ የፈጣሪ አካል ባህርይ በሆነ ጊዜ ፍጹም አምላክነትን አገኘ እንጅ ሃይ አበ ፷፮ ÷ ፲፭

፭, ሕማም ሞት የነበረበት የሌለበት ሆነ ።
ወሥጋሁ አንስአ ሙታነ እለ ሀለዉ ውስተ መቃብር ወነፍሱሂ ፈትሐት ነፍሳተ እንተ ሙቅህቶን ይነብራ ውስተ ሲኦል

ትርጕም፦ ሥጋው በመቃብር ያሉ ሙታንን አስነሳ ነፍሱም በሲኦል ተግዘው የነበሩ ነፍሳትን ፈታች
ሃይ አበ ፳፮ ÷ ፳

ልደታችን ልደቱ ካደረገ ልደቱን ልደት አድርገን ግብሩንም ግብራችን ልናደርግ ይገባናል

እርሱ በቀዳማዊ ልደቱ ሕማም ሞት እንደሌለበት በደኃራዊ ልደቱ ግን ሕማምን ሞትን ገንዘብ እንዳደረገ እኛም በቀዳማዊ ልደታችን መከራ ሕማም የለብንም ቢኖርብንም ረብህ ጥቅም የለውም በሁለተኛው ልደታችን ግን እርሱን የምንመስልበት ልደት ነውና ሕማም መከራ አልብን በዚህም ረብህ ጥቅም እናገኝበታለን
ወእመሰኬ ተመሰልናሁ በሞቱ ንትሜሰሎ በሕይወቱ
በሞት ከመሰልነው በሕይወትም እንመስለዋለን
ሮሜ ፮ ÷ ፭

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

06 Jan, 07:33


እንደ መለኮታዊነቱ ሕፃናትን በእናታቸው ማሕፀን የሚሥል ነው፡፡ እንደ ሰውነቱ ሕፃናት በሚሣሉበት መጠን የተሣለ፣ የተፀነሰ ነው። ያው ግን በተዋሕዶ ነው።
እንደ መለኮታዊነቱ ረቂቅ እምረቂቅ ነው። እንደ ሰውነቱ ግዘፈ ሥጋን መንሳት የተገባው ነው።
እንደ ሰውነቱ በሥጋው ገዝፎ የሚታይ የሚጨበጥ ሁኖ ተወለደ። እንደ መለኮታዊነቱ ማኅተመ ድንድግልናዋን አልለወጠውም።ያው ግን አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው።
እንደ መለኮታዊነቱ ዓለምን በእጁ የያዘ ነው። እንደ ሰውነቱ በድንግል ክንድ መወሰን መታቀፍ ተገባው።
እንደ ሰውነቱ በበረት ተጥሎ በረደው። እንደ አምላክነቱ የማይዳሰስ እሳት ነው። እሳታውያን መላእክትን የፈጠረም እርሱ ነው።
እንደ ሰውነቱ ከድንግል ጡትን መጥባት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ለረቂቁ ረቂቅ፣ ለግዙፉ ግዙፍ ምግብን የሚመግብ ነው።ይሄውም በተዋሕዶ የሆነ ነው።
እንደ ሰውነቱ በሰሎሜ መዳሰስ ተገባው። እንደ አምላክነቱ በእሳትነቱ እጇን ከእሳት እንደ ገባ ጅማት ማቃጠል ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ ወደ ግዝረት ቤት መሄድ ተገባው። እንደ አምላክነቱ ለአብርሃም ግዝረትን የሠራ እርሱ ነው።
እንደ አምላክነቱ ኦሪትን የሠራት እርሱ ነው። እንደ ሰውነቱ ሕገ ኦሪትን መፈጸም ተገባው።
እንደ ሰውነቱ ወደ ግብጽ መሰደድ ተገባው። እንደ አምላክነቱ ዓለምን በመሀል እጁ የያዘ በሁሉ የመላ ነው።
እንደ ሰውነቱ እንጨት በመስበር፣ ውኃ በመቅዳት፣ እሳት በመጫር ለእናት ለዘመድ መታዘዝ ተገባው። እንደ አምላክነቱ ውኃ በወንፊት፣ እንጨት በነፋስ፣ እሳት በልብስ ያደርስላቸው ነበር።
እንደ ሰውነቱ አፈር መፍጨት፣ ውኃ መራጨት፣ ከሕፃናት ጋራ መጫወት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ያቦካውን ጭቃ ወፍ አድርጎ መፍጠር፣ በእግረ ፀሐይ መሄድ፣ ከጫወታው ቦታ የሞተ ሕፃን ማስነሣት ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ ለበዓል ወደ መቅደስ መውጣት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ይህ ያባቴ ቤት ነው አለ።
እንደ ሰውነቱ መድከም ተገባው። እንደ አምላክነቱ ድኩማንን ማበርታት ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ በመርከብ ላይ ማንቀላፋት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ባሕር መገሠጽ ነፋስ ማዘዝ ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ አልዓዛርን ወዴት ቀበራችሁት ብሎ ዐላዋቂነትን መናገር ተገባው፡፡ እንደ አምላክነቱ አልዓዛርን ከመቃብር ውጣ በማለት በሥልጣኑ አዝዞ አስነሣው።
እንደ ሰውነቱ እሞታለሁ ማለት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ነፍሴን ማንም ከእኔ ለይቶ መውሰድ የሚቻለው የለም ማለት ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ አብ ይበልጠኛል ማለት ተገባው። እንደ አምላክነቱ እኔና አብ አንድ ነን ማለት ተቻለው።
ይህ ሁሉ በተዋሕዶ በተዓቅቦ የተከናወነ ነው። ተዋሕዶ ያለ ተዓቅቦ ተዓቅቦም ያለ ተዋሕዶ አይነገርም። ሥለ ሥጋው በተናገርነው መለኮት በሥጋው ማለት ነው። ስለ መለኮቱ የተናገርነው ሥጋ በመለኮቱ ማለት ነው።"ተዋሕዶ በተዓቅቦ" ማለት ይሄ ነው።
ወልደ አብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ በተዓቅቦ ከበረ።
ያለተዋሕዶ ተዓቅቦ
የለም፤ ያለ ተዓቅቦም ተዋሕዶ የለም።
ቃል የተዋሐደውን ትስብእትን
ከፍሎ የራሱ አካል ሳያደርገው ያለፈ አንዳችም የጊዜ ቅጽበት የለም። ሲከፈልም፣
ሲዋሐድም፣ ሥጋ በቃል ሲከብርም፣ ቃል ለሥጋ በተዋሕዶ ክብር ሲሆንም አንድ
ጊዜ እንደ ዓይን ጥቅሻ በሆነ ቅጽበት ነው።
በቅጽበት በሆነው የባሕርይ ተዋሕዶም
ተዓቅቦ እንጂ ሁለትነት የለበትም።የቃል እና የሥጋ በተዋሕዶ መገናዘብ አንድ ጊዜ ነው።ድኅረም ቅድመም የለውም።ጊዜ ተዋሕዶ በቅጽበት የተፈጸመ ተዓቅቦን ያላጠፋ አንድነት ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

06 Jan, 07:33


             "ተዋሕዶ በተዓቅቦ"
        "ቃል ሥጋ ሆነ" ዮሐ.፩፥፲፬
በኋላ ዘመን  የቀጠሮጊዜው ሲደርስ እግዚአብሔር በልብ የመከረውን በነቢያት ያናገረውን ለመፈጸም  ከሦስቱ አካላት አንዱ አካላዊ ቃል ሥጋ ሆነ።ድኅነተ ዓለም ሊፈጸም ቅድስት እመቤታችን ማርያም በተወለደች በ፲፭ ዓመቷ ይኸውም ዓለም በተፈጠረ ዘመን በተቆጠረ በ፶፻፭፻ ዘመን ሲፈጸም በዘመነ ዮሐንስ በወርኃ መጋቢት በዕለተ እሑድ ከነግሁ በሦስት ሰዓት
በብሥራተ መልአክ “ከመ ቅጽበተ ዓይን በዘ ኢይተረጎም- እንደ ዓይን ጥቅሻ በማይመረመር
ምሥጢር” ሃይ.አበ. ፻፮፥፲፫ ከእርሷ ሰው ሆነ። በረቂቅ ጥበቡ በመጠነ ሕፃናት ተፀነሰ። ዮሐ. ፩፥፲፬፤
በ፶፻፭፻፩ ዓመት በገጸ ብእሲ በተመሰለ በዘመነ ማቴዎስ በወርኃ ታኅሣሥ በ፳፱ ቀን በዕለተ ሠሉስ ከሌሊቱ
በ፲ ሰዓት የአጥቢያ ኮከብ ሳይወጣ ቃል በሥጋው በተዋሕዶ ከቅድስት ድንግል ተወለደ። መዝ. ፻፱፥፫
በተዋሕዶውም ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆነ።ይሄውም ፍጹም ተዋሕዶው በተዓቅቦ የጸና ነው እንጂ በመጠፋፋት የተፈጸመ ኩነት አይደለም።
ቅድስት እመቤታችን "ይኩነኒ-እንዳልኸኝ ይሁን"ስትል ፈቃዷን ምክንያት አድርጎ ከድንግልናዊ አካል ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነሥቶ በድንቅ ምሥጢር የቃል አካል እና የሥጋ አካል በተዋሕዶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆነ።
የቃል እና የሥጋ ተዋሕዶ ያለመጠፋፋት፣ያለ መለወጥ፣ያለ ሕድረት፣ያለ ፍልጠት፣ያለ ሚጠት የተፈጸመ ዘለዓለማዊ ተዋሕዶ ነው።ከተዋሕዶ በኋላ በተዓቅቦ ምሥጢር ይነገራል እንጂ ይህ የቃል ነው ይሄ ደግሞ የሥጋ ነው የሚባል የየብቻ ግብር የለም።"ተዋሕዶ አእተታ ለምንታዌ-ተዋሕዶ ሁለትነትን አጠፋት" እንዲል።ተዋሕዶ ሁለትን አጥፍቶት የቃል ገንዘብ ለሥጋ የሥጋም ገንዘብም በተዋሕዶ ለቃል ገንዘቡ ሁኗልና።
የሥጋ ገንዘብ የሆነውን ግዙፍነትን፣ውሱንነትን፣ርኩብነትን፣..የመሳሰለውን ሁሉ በተዓቅቦ  ቃል ገንዘብ አደረገው። የቃል ገንዘቡ የሆነውን፦ረቂቅነትን፣ምሉዕነትን፣ሕያውነትን፣..የመሳሰለውን ሁሉ ሥጋ በተዓቅቦ ገንዘብ አደረገው።ይሄንን የመሰለውን ቅድመ ተዋሕዶ በተነበረ ግብር እያዩ አንድ አካል አንድ ባሕርይ መሆኑን ሳይነዱ ቢተረጉሙት ግን ምሥጢረ ሥጋዌ ይፈልሳል።ሳያዋሕዱ እና በተዓቅቦ አጽንተው በሥጋ ገንዘብ ወይም በቃል ገንዘብ ብለው ባይናገሩ  ምንፍቅና ይሆናል።
ሰው ሆነ፣በየ ጥቂቱ አደገ፣ተራበ ተጠማ፣አዘነ ተከዘ፣ታመመ ሞተ፣ተቀበረ ተነሣ፣ቶማስ ዳሰሰው፣እያዩት ዓረገ፣ዳግመኛ በግርማ መለኮት በክበበ ትስብእት አሠረ ቅንዋቱን ሳያጠፋ ይህንን ዓለም ለማሳለፍ ይመጣል..የምንለው ቃልን በሥጋው ገንዘብ በተዋሕዶ በተዓቅቦ መናገራችን ነው። በአንጻሩ ሥጋን በተዋሕዶ ምሥጢር በመለኮቱ ገንዘብ፦ሕያው ማሕየዊ፣ከሀሌ ኲሉ፣ፈጣሪ፣ቀዳማዊ፣...በተባለበት ርሥት ሥጋ ሲነገርለት በተዋሕዶ በተዓቅቦ ሥጋ በቃል ገንዘብ ያገኘው ነው።
ይሄውም ጠቅለል ብሎ ሲገለጽ፦በተዋሕዶ የቃል ገንዘብ ለሥጋ ሁኗልና ሥጋ በመለኮቱ ተብሎ ይነገርለታል።የሥጋም ገንዘብ ለቃል ሁኗልና ቀል በትስብእቱ ተብሎ ተዓቅቦ በተዋሕዶን ሳይለቅ ይነገርለታል።
በተዋሕዶው ፍልጠት፣ በተዓቅቦው መጠፋፋት የለበትም። የአብ ልጅም እርሱ አንዱ ነው፤ ድንግል በሥጋ የወለደችውም እርሱ አንዱ ነው። ቅድመ ዓለም በመለኮቱ ከአብ ድኅረ ዓለም በትስብእቱ ከድንግል ማርያም ተወለደ።
በዕለተ ትስብእት እንደ ዐይን ጥቅሻ በድንቅ ምሥጢር፦
[  ] እንደ ቃል እና እንደ ቀለም ተዋሐደ፡፡ በልቡና ያለ ቃልን በብራና በሣሉት፣ በጻፉት ጊዜ ርቀቱን ሳይለቅ በብራናው ላይ አካል ገዝቶ  እንዲታይ፤ አካላዊ ቃልም ርቀቱን ሳይለቅ በተዋሕዶ ግዘፈ ሥጋን ግዘፈ አካልን ገንዘብ አደረጎ ታየ። ብራና በተጻፈበት ቃል ርቀት እንዲነገርለት ሥጋም በቃል ገንዘቡ ረቂቅ አካለ ቃልን በተዋሕዶ ገንዘብ አድርጓልና ተዓቅቦን ሳይለቅ ረቂቅ ቃልን ገንዘብ አደረገ ብለን እናምናለን። ሃይ.አበ. ፶፫፥፲፫
[  ] እንደ ብረት እና እንደ እሳት ምሳሌ ባለ ተዋሕዶ ተዋሐደ። ቀዝቃዛ ብረት ወደ እሳት በተጣለ ጊዜ የእሳትን ገንዘብ ተቀብሎ እንዲያቃጥል፤ እሳትም በብረቱ ገንዘብ ተወስኖ በጉጠት እንዲያዝ፤ ሥጋ በቃል ገንዘብ በተዋሕዶ ሕያው መለኮት ተባለ። ቃልም በሥጋ ገንዘብ ተዳሰሰ መከራ ተቀበለ።ሃይ.ቄር. ፸፫፥፲፪፣
[  ] እንደ ነፍስ እና እንደ ሥጋ ባለ ተዋሕዶ ተዋሐደ።ግዙፍ ሥጋ ከረቂቅ ነፍስ፣ ረቂቅ ነፍስም ከግዙፍ ሥጋ ጋር ባለ መጠፋፋት በተዋሕዶ፣ በተዓቅቦ ጸንተው በአንድ አካልነት እንዲገለጹ ቃልና ሥጋም እንደ ነፍስ እና እንደ ሥጋ ባለ የተዓቅቦ ተዋሕዶ ተዋሐዱ፤ ሁለትነትም ጠፍቶ አንድ ባሕርይ አንድ አካል ሆነ። ሃይ.አበ.ቄር. ፸፫፥፲፱
[  ] እንደ ባሕር እና እንደ ርጥበት ባለ ተዋሕዶ ተገለጸ። ከውኃ የገባ ሰው የውኃውን ርጥበት ገንዘብ አድርጎ በሰፊው ባሕር እንዲገለጽበት፣ በርጥበቱ ሞላ እንዲባል፣ ርጥበተ ባሕርም በአካሉ እንዲወሰን ሥጋም ቃልን በተዋሕዶ  በተዓቅቦ ገንዘብ አድርጎ በሁሉ የመላ ሆነ። ቃልም በተዋሕዶ በሥጋው  ተዓቅቦን ሳይለቅ ምልዓቱ ሳይጠፋ በሥጋው ተወሰነ። አረ.መን.ድር. ፳፪
[  ] እንደ ፈትልና እንደ እሳት ባለ ተዋሕዶ ተገለጸ። እሳት በፈትል ላይ ተወስኖ፣ ፈትልም በእሳት ብርሃን መልቶ እንዲገለጽ፤ ቃል በሥጋው ተወሰነ። ሥጋም በቃልነቱ ምሉዕ በኵለሄ ተባለ። ራእ. ፲፭፥፫
[  ] እንደ ዓይን እና እንደ ፀሐይ ባለ ተዋሕዶ ተዋሐደ። የዓይን ብሌን በብርሃነ ፀሐይ መልቶ እንዲያይ፣ ብርሃነ ፀሐይም ምልዓቱን ሳይለቅ በዓይናችን ብሌን መጠን ተወሰነ እንዲባል፤ ሥጋም በቃል ገንዘብ ከበረ፡፡ ቃልም ለሥጋው ክብር ሲሆን በሥጋ ገንዘብ ወረሰ ሀየሰ ነግሠ መባልን ገንዘብ አደረገ።  ሃይ.አበ. ዮሐ. ፻፯፥፲፮
ለድንቅ ተዋሕዶው እንደሚገባ የሚገልጽ ምሳሌ አይገኝም።በዘየሐጽጽ ምሳሌ መናገር ነው እንጂ።ከጥበቡ በሚበልጥ ጥበቡ ሰውን ያድን ዘንድ ሰው መሆኑ እጅግ ረቂቅ ነው። ይህ ምሥጢር በመላእክት በደቂቀ አዳም ህሊና አቅም ሊታወቅ ሊመረመር የሚችል ምሥጢር አይደለም።"ወላዕለ ኲሉ ህሊናት-ከህሊናት ሁሉ በላይ ነው እንጂ"
በመላው ዘመነ ሥጋዌ እግዚአብሔር ቃል መለኮቱን ከትስብእቱ፣ ትስብእቱን ከመለኮቱ በተዋሕዶ በመግለጽ ያስረዳበት ዘመን ነው። ብቻ የሥጋን ብቻ የመለኮትን ነገር የገለጸበት ዘመን አይደለም።በተዋሕዶ መለያየት የለምና ከፅንሰቱ እስከ ዕርገቱ ድረስ ተዋሕዶ በተዓቅቦን የገለጸበት ዘመን ነው እንጂ። የድካምን ነገር ለትስብእቱ ብቻ፤የኃይል ነገር ለመለኮቱ ብቻ አንሰጥም።በተዋሕዶ በተዓቅቦ የተፈጸመ እንደመሆኑ መጠን መለኮት በሥጋው፤ሥጋ በመለኮቱ እያልን በተዋሕዶ እንናገራለን እንጂ።ከተዋሕዶው የተለየ ምንም አይነት የተለያየ ተግባር የለም።ለምሳሌ፦
አንዱ አካል እርሱ እንደ መለኮታዊነቱ በኅቱም ድንግልና በሰሚዕ መፀነስ ነው፡፡ እንደ ሰውነቱ የዕለት ፅንስ መሆን ነው፤
እንደ መለኮታዊነቱ ብሉየ መዋዕል ነው፣ እንደ ሰውነቱ በፅንሱ በዘመን መቆጠር ተገባው፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Jan, 07:55


የሳምንቱ መታሰቢያ ኖላዊ(እረኛ)ነው።
በኖላዊነት ደረጃ፦አምላካዊ፣መልአካዊ፣ነቢያዊ፣ንጉሣዊ፣ካህናዊ እረኝነቶች አሉ።
አሁን ባለው በሐዲስ ኪዳን በዋናነት ከክርስቶስ የኖላዊነት አደራውን የተቀበሉ ሐዋርያት ናቸው።
ቅዱሳን ሐዋርያት እረኝነትን የተቀበሉት በፍቅር ሁነው ነው።
ለዚህም በቅዱስ ጴጥሮስ በኩል፦
"የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ ትወደኛለህን? አለው።አዎን ጌታ ሆይ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ግልገሎቼን አሰማራ አለው።ደግሞ ሁለተኛ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ ትወደኛለህን? አለው።አዎን ጌታ ሆይ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ጠቦቶቼን ጠብቅ አለው።ሦስተኛ ጊዜ። የዮና ልጅ ስምዖን ሆይ፥ ትወደኛለህን? አለው። ሦስተኛ። ትወደኛለህን? ስላለው ጴጥሮስ አዘነና። ጌታ ሆይ አንተ ሁሉን ታውቃለህ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ አለው። ኢየሱስም። በጎቼን አሰማራ።"ዮሐ.፳፩፥፲፭ ብሏቸዋል።
በዚህ መልኩ ቅዱሳን ሐዋርያት ወደው ፈቅደው በበግ የተመሰሉ የእግዚአብሔር ልጆችን እንዲጠብቁ ተወክለዋል።
በዚህ ድንቅ የኖላዊነት ሕይወት ለብዙ ዘመናት ለረጅም ወራት እረኞች በጎቻቸውን ሲጠብቁ ኑረዋል።
አሁን አሁን ደግሞ በተገላቢጦሽ እረኛቸውን ቀበሮ እንዳይበላው የሚጠብቁ ከጠፋበት የሚፈልጉ በጎችን እየተመለከትን ነው።
በጎቻቸውን የሚጠብቁ የሚፈልጉ እረኞች ግን ሁሉም ባይባልም ከእረኛ ወደ ምንደኛ ተሸጋግረዋል።
ይሄ የእረኛው ትንቢታዊ ተረት የደረሰ ይመስላል፦
"የበጎች እረኛ አያ ሞኙ ሞኙ።
አንተ ጠፋህ እንጂ በጎቹስ ተገኙ።" የሚለው።
መንጎችን ለመባያነት፣ለምግብ፣ለቅጥር..ማብ መጨነቅ ትልቅ ምንደኝነት ነው።
ምንደኛ ደግሞ ቅጥረኛ ስለሆነ ሆዱ ከጎደለ በጎቹን መጠበቅ አይፈልግም።በነቢይ አድሮ የተናገረው ቃል እግዚአብሔር በእረኞች ማዘኑን የሚገልጽ ነው።
"ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል እኔ ሕያው ነኝና እረኛ ስለሌለ እረኞቼም በጎቼን ስላልፈለጉ እረኞችም ራሳቸውን እንጂ በጎቼን ስላላሰማሩ በጎቼ ለንጥቂያ ሆነዋልና በጎቼም ለምድር አራዊት ሁሉ መብል ሆነዋል።" ሕዝ.፴፬፥፰
ጎበዝ ቢቻል በትክክል በጎችን መጠበቅ ይገባል።ካልሆነ እንኳ አሳልፎ ለተኩላ መስጠቱ ለምንድን ነው?
ባለቤት የሌለው ቤት ሆነና በጎች፦ በነጋዴዎች፣በነጣቂዎች፣በሸላቾች፣በቄራዎች ..እጅ ወደቁ።
እግዚአ ኖሎት ክርስቶስ ለሁሉ እንደየሥራው ሊሰጠው በተገለጸ ጊዜ ግን ፍትሁን ማን ይችለዋል?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Jan, 07:52


ከላይ ያለው ለዘመነ ሥጋዌ መሰንበቻ የተጻፈ ምሥጢረ ሥጋዊ ነው።በጥብቅ እንመልከተው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Jan, 07:37


የአንዲት ባሕርይ ፈቃዳዊ ግብር ነውና ደም ድንግልናዊን መክፈል በሦስቱም
ፈቃድ ተከናወነ።
ሥጋን መክፈል፣ ሥጋን ማዋሐድ፣ ሥጋን በአንዲት ተገናዝቦ
በአንዲት ባሕርይ ማክበር የሦስቱ አካላት የአንዲት ሥልጣን እና የተገናዝቦ ግብር
ነው። ይህም ማለት መክፈል፣ ማዋሐድ የአንዲት ባሕርይ ሥልጣን ግብር ነው።
ማክበር ደግሞ የነሢእ ተገናዝቦ ከዊናዊ ግብር ነው። መወሐድ ለቃል ለሥጋ
ይነገራል። ቃልም ሥጋን ተዋሕዷል፤ ሥጋም ቃልን ተዋሕዷልና።
በተዋሕዶ ግብር
ለሥጋው ክብር መሆን ግን የወልድ የተለየች የተዋሕዶ ኩነት ናት። መከፈል፣
መክበር የሥጋ ግብር ነው። ወልድስ ሰው ሁኗልና በኩነተ-ሥጋ፣ በተዋሕዶቱ፣
በተዓቅቦ ለሥጋው ክብር ሆነው፣ አከበረው እንላለን። አብና መንፈስ ቅዱስ ወልድ የተዋሐደው ሥጋን እንዴት አከበሩት ቢባል? አብና መንፈስ ቅዱስ ያ አካላዊ ቃል
የተዋሐደው ሥጋ በተዋሕዶ፣ በተዓቅቦ የቃል ገንዘብ ለሥጋ ሁኖ አንድ አካል አንድ ባሕርይ በመሆን ሁለትነት የለምና
በኩነት ግብር በቃልነቱ ይገናዘቡታል። እርሱም በህልውናው በቃልነቱ ከዊን ግብር በነሢእ
በተገናዝቦ ገንዘብ ያደርጋቸዋልና ስለዚህ ነው። ያ ቃልን የተዋሐደ ሥጋ በቃል
ገንዘብ በተዋሕዶ ለአብ እና ለመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው። ለዚያ ሥጋም በቃልነቱ
ገንዘብ አብ የባሕርይ ልቡ መንፈስ ቅዱስ ደግሞ የባሕርይ ሕይወቱ ነው።
በጠቅላላው ግን በዚህ ምሥጢር ይዘት ላይ ለእግዚአብሔር ቦታ መስጠት
ይጠይቃል።
ሥላሴ በማሕፀነ ድንግል ስላደረጉት ድንቅ ምሥጢር የተገለጸውን
ያህል ጥቂት እንናገራለን እንጂ የግድ ሁሉ መታወቅ አለበት አያሰኝም። ከታወቀው
ከተጻፈው መናገር እንጂ።
በፍጡራዊ አእምሮ ካወቅነውማ ምኑን ምሥጢር ሆነው?
“መንክር ውእቱ ልደትከ ኦ ወልደ እግዚአብሔር- ወልደ እግዚአብሔር ሆይ ልደትህ ድንቅ
ነው” ሃይ.አበ. ፹፰፥፩፣ ኢሳ. ፱፥፮ እንደ ዓይን ጥቅሻ በሆነ ተዋሕዶ እግዚአብሔር
ቃል እና ባሕርየ ሥጋ በአንድ ተዋሕዶ ጸንተው ሁለትነት ጠፍቶ እንደ ዓይን
ጥቅሻ በሆነ ምሥጢር ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ከሁለት አካል አንድ አካል
ሆነ፤ ወልደ አብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ በተዓቅቦ ከበረ።
ያለተዋሕዶ ተዓቅቦ
የለም፤ ያለ ተዓቅቦም ተዋሕዶ የለም። ሁለት አካላት አንድ አካል ሆነ ማለትም
ተዋሕዶው ተጋውሮ ተደምሮ ወይም ተድኅሮ አለበት ማለት አይደለም። ቅድመ
ተዋሕዶ በነበረው ልዩ አካልነት መናገር ነው እንጂ።
ቃል የተዋሐደውን ትስብእት
ከፍሎ የራሱ አካል ሳያደርገው ያለፈ አንዳችም የጊዜ ቅጽበት የለም። ሲከፈልም፣
ሲዋሐድም፣ ሥጋ በቃል ሲከብርም፣ ቃል ለሥጋ በተዋሕዶ ክብር ሲሆንም አንድ
ጊዜ እንደ ዓይን ጥቅሻ በሆነ ቅጽበት ነው።
በቅጽበት በሆነው የባሕርይ ተዋሕዶም
ተዓቅቦ እንጂ ሁለትነት የለበትም።የቃል እና የሥጋ በተዋሕዶ መገናዘብ አንድ ጊዜ ነው።ድኅረም ቅድመም የለውም።ጊዜ ተዋሕዶ የተፈጸመ ተዓቅቦን ያላጠፋ አንድነት ነው እንጂ።
ምክንያቱም፦
ከፍሎ ሳይዋሐድ ቢቆይ ኀደረ በብእሲ በተባለ ነበርና።
ተዋሕዶ ሳይከፍል ቢቆይ እመቤታችን አምላክ ሆነች ባሰኘ ነበርና።
ከብሮ ሳይዋሐድ ቢቆይ በማን ከበረ/በሌላ ከበረ/ በተባለ ነበረና።ወይም ክብር ከክብር ጋራ ተዋሐደ ያስብላል።
ተዋሕዶ ሳይከብር ቢቆይ ዜገ፣አንደየ፣አካለ ቃል ክብር አልባ በተባለ ነበርና።ስለዚህ ሲከፍልም፣ ሲዋሐድም፣ከሁለት አካል አንድ አካል ሲሆንም ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሲሆንም፣በተዋሕዶ በተዓቅቦ ሲገናዘብም አንድ ጊዜ ነው፡፡
በዚህ ምሥጢር መሠረት ቃል ሥጋ ሆነ ሥጋም ቃል ሆነ፡፡ቃል በተዋሕዶ በተዓቅቦ ሥጋ ሲሆን ምልአቱን፣ ጌትነቱን፣ስፍሐቱን፣ ርቀቱን፣ አምላክኘቱን፣ባሕርያዊ ክብሩን ሳይለውጥ ሳይለውጥ ነው።ሥጋም በተዋሕዶ በተዓቅቦ ቃል ሲሆን ውሱንነቱ፣ ጸቢብነቱ፣ ግዘፉን፣ ሰውነቱን ሳይለውጥ ነው፡፡
ይሄም ማለት ያለ ውላጤ፣ ያለ ኅድረ፣ያለ ሚጠት፣ ያለ ቡዓዴ፣ ምሉዕው ውሱን፣ ውሱኑ ምሉዕ፣ ስፉሑ ጸቢብ፣ ጸቢቡ ስፉህ፣ ግዙፉ ረቂቅ፣ ረቂቁ ግዙፍ ሆነ፡፡ ከሁለት አካል አንድ አካል፣ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆነ፡፡ ምንታዌ ጠፋ ፤ አንድነት ጸና፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Jan, 07:37


እንደ ዓይን እና እንደ ፀሐይ ባለ ተዋሕዶ ተዋሐደ። የዓይን ብሌን በብርሃነ ፀሐይ መልቶ እንዲያይ፣ ብርሃነ ፀሐይም ምልዓቱን ሳይለቅ በዓይናችን ብሌን መጠን ተወሰነ እንዲባል፤ ሥጋም በቃል ገንዘብ ከበረ፡፡ ቃልም ለሥጋው ክብር ሲሆን በሥጋ ገንዘብ ወረሰ ሀየሰ ነግሠ መባልን ገንዘብ አደረገ።  ሃይ.አበ. ዮሐ. ፻፯፥፲፮
ከጥበቡ በሚበልጥ ጥበቡ ሰውን ያድን ዘንድ ሰው መሆኑ እጅግ ረቂቅ ነው። ይህ ምሥጢር በመላእክት በደቂቀ አዳም ህሊና አቅም ሊታወቅ ሊመረመር የሚችል ምሥጢር አይደለም።"ወላዕለ ኲሉ ህሊናት-ከህሊናት ሁሉ በላይ ነው እንጂ"
በመላው ዘመነ ሥጋዌ እግዚአብሔር ቃል መለኮቱን ከትስብእቱ፣ ትስብእቱን ከመለኮቱ በተዋሕዶ በመግለጽ ያስረዳበት ዘመን ነው። ብቻ የሥጋን ብቻ የመለኮትን ነገር የገለጸበት ዘመን አይደለም። ከፅንሰቱ እስከ ዕርገቱ ድረስ ተዋሕዶ በተዓቅቦን የገለጸበት ዘመን ነው እንጂ። የድካምን ነገር ለትስብእቱ ብቻ የኃይል ነገር ለመለኮቱ ብቻ አንሰጥም በተዋሕዶ በተዓቅቦ የተፈጸመ እንደመሆኑ መጠን መለኮት በሥጋው ሥጋ በመለኮቱ እያልን በተዋሕዶ እንናገራለን እንጂ ከተዋሕዶው የተለየ ምንም አይነት ተግባር የለም።ለምሳሌ፦
እንደ መለኮታዊነቱ በኅቱም ድንግልና በሰሚዕ መፀነስ ነው፡፡ እንደ ሰውነቱ የዕለት ፅንስ መሆን ነው፤
እንደ መለኮታዊነቱ ብሉየ መዋዕል ነው፣ እንደ ሰውነቱ በፅንሱ በዘመን መቆጠር ተገባው፡፡
እንደ መለኮታዊነቱ ሕፃናትን በእናታቸው ማሕፀን የሚሥል ነው፡፡ እንደ ሰውነቱ ሕፃናት በሚሣሉበት መጠን የተሣለ፣ የተፀነሰ ነው። ያው ግን በተዋሕዶ ነው።
እንደ መለኮታዊነቱ ረቂቅ እምረቂቅ ነው። እንደ ሰውነቱ ግዘፈ ሥጋን መንሳት የተገባው ነው።
እንደ ሰውነቱ በሥጋው ገዝፎ የሚታይ የሚጨበጥ ሁኖ ተወለደ። እንደ መለኮታዊነቱ ማኅተመ ድንድግልናዋን አልለወጠውም።ያው ግን አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነው።
እንደ መለኮታዊነቱ ዓለምን በእጁ የያዘ ነው። እንደ ሰውነቱ በድንግል ክንድ መወሰን መታቀፍ ተገባው።
እንደ ሰውነቱ በበረት ተጥሎ በረደው። እንደ አምላክነቱ የማይዳሰስ እሳት ነው። እሳታውያን መላእክትን የፈጠረም እርሱ ነው።
እንደ ሰውነቱ ከድንግል ጡት መጥባት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ለረቂቁ ረቂቅ፣ ለግዙፉ ግዙፍ ምግብን የሚመግብ ነው።ይሄውም በተዋሕዶ የሆነ ነው።
እንደ ሰውነቱ በሰሎሜ መዳሰስ ተገባው። እንደ አምላክነቱ በእሳትነቱ እጇን ከእሳት እንደ ገባ ጅማት ማቃጠል ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ ወደ ግዝረት ቤት መሄድ ተገባው። እንደ አምላክነቱ ለአብርሃም ግዝረትን የሠራ እርሱ ነው።
እንደ አምላክነቱ ኦሪትን የሠራት እርሱ ነው። እንደ ሰውነቱ ሕገ ኦሪትን መፈጸም ተገባው።
እንደ ሰውነቱ ወደ ግብጽ መሰደድ ተገባው። እንደ አምላክነቱ ዓለምን በመሀል እጁ የያዘ በሁሉ የመላ ነው።
እንደ ሰውነቱ እንጨት በመስበር፣ ውኃ በመቅዳት፣ እሳት በመጫር ለእናት ለዘመድ መታዘዝ ተገባው። እንደ አምላክነቱ ውኃ በወንፊት፣ እንጨት በነፋስ፣ እሳት በልብስ ያደርስላቸው ነበር።
እንደ ሰውነቱ አፈር መፍጨት፣ ውኃ መራጨት፣ ከሕፃናት ጋራ መጫወት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ያቦካውን ጭቃ ወፍ አድርጎ መፍጠር፣ በእግረ ፀሐይ መሄድ፣ ከጫወታው ቦታ የሞተ ሕፃን ማስነሣት ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ ለበዓል ወደ መቅደስ መውጣት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ይህ ያባቴ ቤት ነው አለ።
እንደ ሰውነቱ መድከም ተገባው። እንደ አምላክነቱ ድኩማንን ማበርታት ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ በመርከብ ላይ ማንቀላፋት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ባሕር መገሠጽ ነፋስ ማዘዝ ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ አልዓዛርን ወዴት ቀበራችሁት ብሎ ዐላዋቂነትን መናገር ተገባው፡፡ እንደ አምላክነቱ አልዓዛርን ከመቃብር ውጣ በማለት በሥልጣኑ አዝዞ አስነሣው።
እንደ ሰውነቱ እሞታለሁ ማለት ተገባው። እንደ አምላክነቱ ነፍሴን ማንም ከእኔ ለይቶ መውሰድ የሚቻለው የለም ማለት ተቻለው።
እንደ ሰውነቱ አብ ይበልጠኛል ማለት ተገባው። እንደ አምላክነቱ እኔና አብ አንድ ነን ማለት ተቻለው።
ይህ ሁሉ በተዋሕዶ የተከናወነ ነው። ተዋሕዶ ያለ ተዓቅቦ ተዓቅቦም ያለ ተዋሕዶ አይነገርም። ሥለ ሥጋው በተናገርነው መለኮት በሥጋው ማለት ነው። ስለ መለኮቱ የተናገርነው ሥጋ በመለኮቱ ማለት ነው። እንዲህ እንዲህ እያለ ከፅንሰቱ እስከ ዕርገቱ መላ የነገረ ክርስቶስ አመሥጥሮት በተዋሕዶ በተዓቅቦ መለኮቱ በትስብእቱ፣ ትስብእቱ በመለኮቱ ይገለጻል።ያለ ተዋሕዶ ግን ምንም ግብር አልተፈጸመም በተዋሕዶው አንድ አካል አንድ ባሕርይ ነውና ፈጽሞ መለወጥ የለበትም።ተዋሕዶን ያለ ተዓቅቦ ተዓቅቦንም ያለ ተዋሕዶ መናገርም አይቻልም።ያለ መጠፋፋት የተፈጸመ ምሥጢረ ሥጋዌን ያለ ተዓቅቦ መረዳት አይቻልምና።
ቃለ እግዚአብሔር ጥንቱን ሰው በሆነ ጊዜ ግዕዘ ሕፃናትን አላፋለሰም ነበር።
“ተሥዕለ በጥንተ አካል እንዘ ይትወሐድ ምስለ ቃል- ሥጋ ከቃል ጋር ሲዋሐድ የዕለት
ፅንስ በመሆን ተቀረጸ” ሃይ.አበ. ፺፥፳፫ ሕፃናት በሚፀነሱበት መጠን ተፀነሰ፤ ሕፃናት
በእናታቸው ማሕፀን የሚሥላቸው በሥጋው ተሣለ። በጥንተ አካል ከእናቱ ማሕፀን
ደም ድንግልናዊን ነሥቶ ተጸነሰ።
ይህንንም ሊቁ ሲያብራራው “ፈጣሬ ሕፃናት ንዑሳን
ዘያልሕቅ በበህቅ በከርሥ ወይፈጥር አካላተ ፍጹማነ እንዘ በውስተ ከርሠ አንስት ሶበ ፈጸመ
መልክአ አክሊለ ሥጋሁ ወተፈጸመ ጌራ አባለ ዕበዩ ወሶበ አስተጋብአ ሥጋ መልክዑ ዘከመ የአምር
ፈጸመ ህላዌ ማኅተም በማሕፀን ወገብረ ሥዕለ ሰብእ ፍጹመ ወፈጸመ ሐኒጸ ሥጋሁ መንፈሳዊ
ወአቀመ ሥጋሁ በብዙኅ ብዕል- በሴቶች ማሕፀን ሳሉ ሕፃናትን ፈጥሮ ንዑሳን ሕፃናትን
በማሕፀን በየጥቂቱ የሚያሳድግ የሕፃናት ፈጣሪ የራስ ቅልን ፈጥሮ በፈጸመ ጊዜ
ጌትነቱ የሚገለጥበት የራስ ጸጉርም ተፈጥሮ በተፈጸመ ጊዜ እርሱ ባወቀ ሕዋሳትን
በየመልካቸው አንድ አድርጎ ከራስ ጠጉር እስከ እግር ጥፍር ያለውን ፍጹም አካል
ፈጥሮ በጨረሰ ጊዜ ፍጹም አካሉን በማሕፀን የቀረጸ መልክዓ ሰብእን ፍጹም አደረገ፤
ነፍስ ያለው ሥጋውን ፈጥሮ ፈጸመ፤ በአምላክነት ክብርም አጸናው” ሃይ.አበ. ፹፰፥፪
ብሎ በፅንስ ሰለሆነው ምሥጢረ ሥጋዌ ይነግረናል።
አብ እመቤታችንን አጸናት፣ መንፈስ ቅዱስም አነጻት፣ ወልድ ከሥጋዋ ሥጋን
ከነፍሷ ነፍስን ነሥቶ ተዋሐደ። ይህም ማለት ማጽናት ለአብ ቢነገርም የሦስቱም
የአንዲት ባሕርይ ፈቃድ ግብር ነውና ሦስቱም አካላት አጽንተው። ማንጻት ለመንፈስ
ቅዱስ አድሎ ሰጥቶ ቢነገርም የሦስቱም የአንዲት ባሕርይ ፈቃድ ግብር ነውና
ሦስቱም አካላት ከዘር፣ ከሩካቤ፣ ከሰስሎተ ድንግልና አንጽተው።
ማዋሐድ የሦስቱም
ባሕርያዊ ግብረ ፈቃድ ነውና አንዱን አካል ቃልን ባንዲት ፈቃድ አዋሕደዋል።
መወሐድ እና ለሥጋ በኩነት ተዋሕዶ ክብሩ መሆን ግን በተለየ አካሉ ለወልድ
ናትና በልዩ አካልነቱ ሥጋን ተዋሐደ። ለተዋሐደው ሥጋውም ቃል በኩነት ተዋሕዶ
ክብር ሆነው።
ሥጋን መክፈል ለመንፈስ ቅዱስ አድሎ ሰጥቶ ቢነገርም የሦስቱም

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Jan, 07:37


               "ቃል ሥጋ ሆነ" ዮሐ.፩፥፲፬
በኋላ ዘመን ጊዜው ሲደርስ እግዚአብሔር በልብ የመከረውን በነቢያት ያናገረውን ለመፈጸም  ከሦስቱ አካላት አንዱ አካላዊ ቃል ሥጋ ሆነ።ድኅነተ ዓለም ሊፈጸም ቅድስት እመቤታችን ማርያም በተወለደች በ፲፭ ዓመቷ ይኸውም ዓለም በተፈጠረ ዘመን በተቆጠረ በ፶፻፭፻ ዘመን ሲፈጸም በዘመነ ዮሐንስ በወርኃ መጋቢት በዕለተ እሑድ ከነግሁ በሦስት ሰዓት
በብሥራተ መልአክ “ከመ ቅጽበተ ዓይን በዘ ኢይተረጎም- እንደ ዓይን ጥቅሻ በማይመረመር
ምሥጢር” ሃይ.አበ. ፻፮፥፲፫ ከእርሷ ሰው ሆነ። በመጠነ ሕፃናት ተፀነሰ። ዮሐ. ፩፥፲፬፤
በ፶፻፭፻፩ ዓመት በገጸ ብእሲ በተመሰለ በዘመነ ማቴዎስ በወርኃ ታኅሣሥ በ፳፱ ቀን በዕለተ ሠሉስ ከሌሊቱ
በ፲ ሰዓት የአጥቢያ ኮከብ ሳይወጣ ቃል በሥጋ በተዋሕዶ ተወለደ። መዝ. ፻፱፥፫
በዕለተ ፅንስ በኩነት ተዋሕዶው ከሁለት አካል አንድ አካል ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ ሆነ።ይሄውም ፍጹም ተዋሕዶው በተዓቅቦ የጸና ነው እንጂ በመጠፋፋት የተፈጸመ ኩነት አይደለም።
ቅድስት እመቤታችን "ይኩነኒ-እንዳልኸኝ ይሁን"ስትል በድንቅ ምሥጢር የቃል አካል እና የሥጋ አካል በተዋሕዶ አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆነ።
የቃል እና የሥጋ ተዋሕዶ ያለመጠፋፋት፣ያለ መለወጥ፣ያለ ሕድረት፣ያለ ፍልጠት፣ያለ ሚጠት ነው።ተዋሕዶ በኋላ በተዓቅቦ ምሥጢር ይነገራል እንጂ ይህ የቃል ነው ይሄ ደግሞ የሥጋ ነው የሚባል የየብቻ ግብር የለም።"ተዋሕዶ አእተታ ለምንታዌ-ተዋሕዶ ሁለትነትን አጠፋት" እንዲል።ተዋሕዶ ሁለትን አጥፍቶት የቃል ገንዘብ ለሥጋ የሥጋም ገንዘብም በተዋሕዶ ለቃል ገንዘቡ ሁኗልና።የሥጋ ገንዘብ የሆነውን ግዙፍነትን፣ውሱንነትን፣ርኩብነትን፣..የመሳሰለውን ሁሉ በተዓቅቦ  ቃል ገንዘብ አደረገው። የቃል ገንዘቡ የሆነውን፦ረቂቅነትን፣ምሉዕነትን፣ሕያውነትን፣..የመሳሰለውን ሁሉ ሥጋ በተዓቅቦ ገንዘብ አደረገው።ይሄንን የመሰለውን ቅድመ ተዋሕዶ በተነበረ ግብር እያዩ አንድ አካል አንድ ባሕርይ መሆኑን ሳይነዱ ቢተረጉሙት ግን ምሥጢረ ሥጋዌ ይፈልሳል።ሳያዋሕዱ እና በተዓቅቦ አጽንተው በሥጋ ገንዘብ ወይም በቃል ገንዘብ ብለው ባይናገሩ  ምንፍቅና ይሆናል።
የሥጋዌ ግብርም በተዋሕዶ የቃል ገንዘብ ለሥጋ ሁኗልና ሥጋ በመለኮቱ ተብሎ ይነገርለታል።የሥጋም ገንዘብ ለቃል ሁኗልና ቀል በትስብእቱ ተብሎ ተዓቅቦ በተዋሕዶን ሳይለቅ ይነገርለታል።
"ለሊሁ ፈጠረ ሎቱ ሥጋ ሐዲሰ እምዘርኣ ዳዊት በከመ ተጽሕፈ ወረሰዮ ሎቱ አሐደ ዘእእምቅድስት ሥላሴ-ከዳዊት ባሕርይ ለራሱ አዲስ ሥጋን ፈጠረ  እንደተጻፈ ከሦስቱ አካላት አንዱን ወልድን ሆነ።ሃይ.አበ.፸፯፥፪ እንዲል።
የቃል ገንዘቡ ለሥጋ የሥጋም ገንዘቡ ለቃል ሁኗልና ቅድመ ሥጋዌ የቃል ገንዘብ የነበሩ በተዋሕዶ ለሥጋ የሆኑ ግብራት ባለመጠፋፋት በተዋሕዶ በተዓቅቦ ይገለጻሉ፦
ቀዳማዊነት፦ መነሻ ዘመን የለሽነት፣ ቀዳሚ የሌለው ቀዳሚ።
ምሉዕነት፦ በሁሉ መገኘት፣ የሌለበት አለመኖር፣ ሁሉን ፈጥሮ በሁሉ መኖር፣ ከፍጥረት ባሻገር በህላዌው የማይገታ።             
ኃያልነት፦ አሸናፊነት፤ ኅሊና መላእክትን፣ ኅሊና ሰብእን በኃያልነቱ ከማሰብ የሚገታ።
ረቂቅነት፦ ግዘፍ የለሽነት፣ ጠፈር ደፈር የማይከለክለው፤ በረቂቅነቱ ኅሊና መላእክትን የሚያገዝፍ።
ባዕልነት፦ የሁሉ ባለቤት፣ የሚያጣው የሌለ፣ ሁሉ በእጁ ሁሉ በደጁ የሆነ፣ ያልቅብኛል የሚለው ነገር የሌለው ፍጹም ባዕል።
ፍቅርነት፦ ከበጎው ነገር የሚጠላው የሌለው፣ ሁሉን ያለ ጥቅም የሚወድ፣ ፍቁረ ባሕርይ።
ሕያውነት፦ ሞት አልባነት፣ በዚህ ጊዜ ያልፋል የማይባል፣ ዘለዓለማዊ ደኀራዊ፣ መዳረሻ የለሽ ሕያው።
ከሀሊነት፦ ሁሉን የሚችል ኃያል፣ ፍጥረቱን ሁሉ ካለመኖር ወደመኖር የፈጠረ፣ እንደገናም ከመኖር ወደ አለመኖር የሚያሳልፍ፣ ያቅተኛል የሚለው የሌለው።
መጋቢነት፦ እንዳሻው ለሁሉ የሚሻውን የሚሰጥ፣ ለረቂቁ ረቂቅ፣ለግዙፉ ግዙፍ ምግብን የሚመግብ፣ አራቱን ባሕርያት ለአራቱ ባሕርያት ምግብ አድርጎ የሚያስማማ።
ጠባቂነት፦ ሳያውቅ ምንም የማይጠፋበት፣ በነፍስ በሥጋ የሚያጸና፣ ማንም ከእጁ የሚቀማው የሌለው ትጉህ እረኛ።
አለመራብ፦ ምግብ የማይሻ፣ ሁሉን የሚመግብ፣ በምክንያት የማይኖር፣ የሚያጸናው የሌለው ጽኑዐ ባሕርይ።
አለመጠማት፦ ጽምዕ የማይስማማው፣ ሁሉን የሚያረካ፣ ውኃን የፈጠረ፣ ረኀብ ጽምዕ የማይስማማው ረቂቅ አካል።
አለመድከም፦ ኃይሉ የማይቀነስበት፣ እቀፉኝ ደግፉኝ የማይል፣ ምክንያት አልባ።
አለማንቀላፋት፦ እንቅልፍ የማይስማማው፣ ሁሉን ጠባቂ፣ ንቁሐ ባሕርይ።
ዐዋቂነት፦ ሁሉ የማይሠወረው፣ ሁሉን ገና ከመሆኑ አስቀድሞ ሳይሆን የሚያውቅ፣ እርሱ ግን በባሕርዩ የማይታወቅ ሁሉን ዐዋቂ ወዘተ… የመሳሰለው የቃል ገንዘብ ሁሉ ተዓቅቦ ባለው ተዋሕዶ የአካላዊ ቃል ገንዘብ በኩነት ተዋሕዶ ለሥጋ ገንዘቡ ሆነ፡፡ ሁለትነት ጠፋ፤ ሥጋ በቃል ገንዘብ አምላክ ወልደ አምላክ ተባለ፤ ከዘመን ተቀድሞ ("ድ"ይጠብቃል) በቃልነቱ በቅድምና ተገኘ፣ የሁሉ ባለቤት ሆነ። ከላይ የዘረዘርናቸውን እና ያልዘረዘርናቸውን የቃልን የባሕርይ መገለጫ ገንዘቦች ሁሉ በተዋሕዶ ሥጋ ገንዘብ አድርጓልና  በተዋሕዶ በተዓቅቦ ይህ ቀረህ የማይባል የሁሉ አምላክ የሁሉ ጌታ ያለ እና የሚኖር ሁሉን ያመጣ ሁሉን ማሳለፍ የሚቻለው ሆነ።
ደግሞም እንደ ቃል ሁሉ በተዋሕዶ የሥጋ ገንዘቦች ከኃጢአት በስተቀር በተዋሕዶ ለቃል ሥግው በፈቃዱ (ወዶ ባደረገው ቸርነት) ገንዘቦች ሆኑ። "ምኩር በኵሉ አምሳሊነ ዘእንበለ ኃጢአት ባሕቲታ- ከብቻዋ ከኃጢአት በስተቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ" ዕብ. ፬፥፲፭ ተብሎ እንደተጻፈ። ቅድመ ሥጋዌ ቅድመ ተዋሕዶ የሥጋ ገንዘቦቹ፦
ደኀራዊነት፦ ኑሮ ኑሮ የተገኘ፣ የኋለኛ ፍጥረት፣ መነሻ ያለው።
ውሱንነት፦ በቦታ የተገደበ፣ ምልአት የለሽ፣ ጠፈር ደፈር፣ ግድግዳ የሚያስቀረው።
ጠባብነት፦ ፍጥረቱን የማይወስን፣ እርሱ በዓለም ውስጥ፣ በቤት ውስጥ የተወሰነ፣ ትንሽ አካል።
ደካማነት፦ ኃይል አልባ፣ ድካም የሚስማማው፣ ጽንአት የሌለው።
ግዙፍነት፦ አረፍት ተራራ የሚከለክለው፣ ነፍስ የተዋሐደችው እርጥብ ሥጋ።
መዋቲነት፦ አለመኖር የሚስማማው፣ ነፍሱ ከሥጋ ሊለይ የሚችል።
ሁሉን አለመቻል፦ የሚሳነው ያለ፣ ደካማ ፍጥረት፣ አቅም የለሽ።
ተመጋቢነት፦ ካልበላ መኖር የማይችል፣ ርኁብ፣ በምግብ የሚጸና።
ተጠባቂነት፦ ራሱን በራሱ በሥውር በግልጥ ከሚመጣበት መከራ ማዳን የማይችል፣ ጠብቁኝ ባይ።
ርኁብነት፦ የጧቱ ለማታ የማታው ለጧት የማይቆይለት፣ ምግብ የሚሻ።
ተጠሚነት፦ በሚጠማ ባሕርይ የሚመላለስ። 
ዐላዋቂነት፡- ድንቁርና የሚስማማው ወዘተ...የመሳሰሉት ናቸው፡፡
አካላዊ ቃል የሥጋ የሥጋን ባሕርይ መገለጫዎች የፈጸማቸው በፈቃዱ ነው።
ተዋሕዶ በተዓቅቦ ሁለትነት ስላጠፋው ሥጋ የቃልን ገንዘብ፤ ቃል የሥጋን ገንዘብ በተዓቅቦ ገንዘብ አደረገ። ሁለትነት በተዋሕዶ በተዓቅቦ  ጠፋ። በተዓቅቦ ጸንቶ ባለመጠፋፋት አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆነ፡፡ "ተዋሕዶ አእተታ ለምንታዌ- ተዋሕዶ ሁለትነትን አጠፋ" እንዲል፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

04 Jan, 07:37


ድኅረ ሥጋዌ
ከተዋሕዶ በኋላ በሥጋው የዘረዘርናቸውን ግብራት በፈቃዱ እንጂ በግድ አይፈጽማቸውም። ለምሳሌ፦ ለሥጋ ረኀብ ይስማማዋል፤ ከተዋሕዶ በኋላ ግን የማይራብ መለኮት ገንዘቡ ነውና የግድ ይራብህ አንለውም። ተራበ የሚል አንቀጽ ብናገኝ በፈቃዱ ወዶ ያደረገው ነው እንጂ ተገዶ ያደረገው አይደለም። እኛን ረኀብ በግድ ያሸንፈናል፤ እርሱ ግን በፈቃዱ ይራባል እንጂ በግድ አይራብም፡፡ ይሄውም ግዕዘ ሰብእን ስላላፋለሰ ነው።ራበኝ ያለም ራሱ ነው የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ ያለም ራሱ ነውና።
በየትኛውም ዘመን በየትኛውም ጊዜ በተዋሕዶ መለወጥ የለም።አንድ አካል አንድ ባሕርይ በተዋሕዶ ሁኗልና ተዓቅቦን ፈጽሞ አላጠፋም። "ዘከመ ፈቀደ ፈጠረ ሰብአ እምድንግል ወለብሰ ወተወሐደ ምስሌሁ ወወጽአ ዮም ወኢያስተተ ሕጸጸ ህላዌነ ወኢረሰየ ሎቱ ሕጸተ ሶበ ለብሰ አባሎ ወዳዕሙ ፍጡር ረብሐ ስብሐተ ዓቢየ ሶበ ኮነ ልብሶ ለፈጣሪ- እንደ ወደደ ከድንግል ነፍስን ሥጋን ፈጥሮ ለበሰ፤ ርሱንም ተዋሕዶ ዛሬ ተወለደ፡፡ ህጸጽ ያለበት ነው ብሎ ባሕርያችንን አልተወውም፡፡ ሥጋን በተወሐደ ጊዜ ቃል ከምልዓቱ አልተወሰነም። ሥጋ የፈጣሪ አካል ባሕርይ በሆነ ጊዜ ፍጹም አምላክነትን አገኘ እንጂ።" ሃይ.አበ. ፷፮፥፱ እንዲል።
ተዋሕዶ በተዓቅቦን ለመረዳት ያክል፦ሰው እንደመሆኑ የዕለት ፅንስ ሆነ፤ አምላክ እንደ መሆኑም በድንግልና ተጸነሰ። ማቴ. ፩፥፲፰ የዕለት ፅንስ የሆነም እርሱ ነው፤ በሰሚዕ ያለ ዘርዐ ብእሲ የተፀነሰም እርሱ ነው። ሉቃ. ፩፥፳፯ በተዓቅቦው መለወጥ የለበትምና።
ሰው እንደ መሆኑ በማሕፀነ ድንግል ተወሰነ፤ አምላክ እንደ መሆኑም በሁሉ ምሉዕ ነው። ኢሳ. ፷፮፥፩ በማሕፀነ ድንግል የተወሰነም አንዱ እርሱ ነው፤ በምልአት ያለም አንዱ እርሱ ነው።
ሰው እንደመሆኑ ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ሲፈጸም በሕፃናት መጠን ተወለደ፤ የዕለት ሕፃን ሆነ። ገላ. ፬፥፬ አምላክ እንደ መሆኑም ማኅተመ ድንግልናዋን አልለወጠም። ሕዝ. ፵፬፥፪
የዕለት ሕፃን የሆነም አንዱ እርሱ ነው፤ ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይለውጥ የተገኘም አንዱ እርሱ ነው። በተዋሕዶው ለውጥ የለበትምና። ሃይ.አበ. ፷፥፲፫፣ ሕዝ. ፵፬፥፩-፬
ሰው እንደ መሆኑ ሰሎሜ ዳሰሰችው፤ አምላክ እንደመሆኑ ሰውነቷን ያቃጠላት እርሱ ነው። የተዳሰሰም የሚያቃጥልም አንዱ ነው።
ሰው እንደ መሆኑ አፈር ሊፈጭ ጭቃ ሊያቦካ ከሕፃናት ጋራ ሊጫወት ወጣ፤ አምላክ እንደ መሆኑ በአውታረ ፀሐይ ይሄዳል፤ የፈጨውን ጭቃ ወፍ አድርጎ ይፈጥር ነበር። ሁሉንም አላፋለሰም በሰውነቱ ስንፈልገው ከመለኮት ጋር ተዋሕዶ እናገኘዋለን። በመለኮቱም ስንፈልገው ከትስብእቱ ጋር ተዋሕዶ በአንድ አካልነቱ ሲገለጽ እናገኘዋለን።
እንደ ሰውነቱ ጠማኝ ሲል እናገኘዋለን፤ እንደ መለኮቱ የሕይወት ውኃ እኔ ነኝ ሲል እናገኘዋለን። ያው ግን ጠማኝ ያለም የሕይወት ውኀ ነኝ ያለም አንዱ አካል ነው። እንደ ሰውነቱ ራበኝ ሲል እናገኘዋለን፤ እንደ መለኮቱም የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ ሲል እናገኘዋለን። በተዋሕዶው ግን ለውጥ የለበትም። ያንቀላፋም ራሱ ነው፤ ከእንቅልፉ ተነሥቶ ባሕሩን የገሠፀውም እርሱ ነው። አልዓዛርን የት ቀበራችሁት? ብሎ የጠየቀም እርሱ ነው። አልዓዛር አልዓዛር ከመቃብር ውጣ ብሎ በኃይሉ ያዘዘውም እርሱ ነው፡፡
እሞታለሁ እሰቀላለሁ ያለም እርሱ ነው፤ ነፍሴን ያለ ፈቃዴ መውሰድ የሚቻለው የለም ያለም እርሱ ነው፡፡ ከእኔ አባቴ ይበልጣል ያለም እርሱ ነው፤ እኔ እና አብ አንድ ነን ያለም እርሱ ነው።
ጌታችን ግዕዘ ሕፃናትን አላፋለሰምና የዕብራውያንን ሕግ እየተማረ አድጓል። "ወተምህረ ሕገ ዕብራውያን- የዕብራውያንን ሕግ ተማረ" እንዳለ አባ ሕርያቆስ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም "ወገብረ በሕገ ኦሪት ከመ ይሣየጦሙ ለእለ ውስተ ኦሪት- በኦሪት ያሉትን ገንዘብ ያደርጋቸው ዘንድ የኦሪትን ሥራ ሠራ" ገላ. ፬፥፬ ብሎታል። ሉቃስ ወንጌላዊም “ወኢየሱስ ልህቀ ወዓብየ በጥበብ ወበምክር ወበጸጋ በኀበ እግዚአብሔር ወበኀበ ሰብእ- ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር" ሉቃ. ፪፥፶፪ ያለው ግዕዘ ሕፃናትን ሳያፋልስ ስላደገ ነው። በዚህ ዓለም የሚወለዱ ሕፃናት ሁሉ ልህቀት መንፈሳዊ ባለበት በዚህ መንገድ ያድጉ ዘንድ በአርአያነቱ አመልክቷል።
በተዋሕዶው ፍልጠት፣ በተዓቅቦው መጠፋፋት የለበትም። የአብ ልጅም እርሱ ነው፤ ድንግል በሥጋ የወለደችውም እርሱ ነው። በመለኮቱ ከአብ በትስብእቱ ከድንግል ማርያም ተወለደ። "ከድንግል በተወለደ ጊዜ ድንግልናዋን ያለመለወጥ አጸናው፡፡ ቀድሞ ሔዋን ድንግል ነበረችና፤ ዲያብሎስ አሳታት እንጂ፡፡ ድንግል ማርያምን ግን ገብርኤል አበሠራት፡፡ ነገር ግን ሔዋንን ዲያብሎስ አሳታት፤ የሞት ምክንያት የሚሆን ቃየልን ወለደች፡፡ ማርያም ግን መልአክ ባበሠራት ጊዜ ሁሉን ወደዘለዓለም ሕይወት የሚመራ አካላዊ ቃልን በሥጋ ወለደችው፡፡ የሔዋን ዕፀ በለስን ልብላ ማለቷ የሞት ምክንያት እንደሆነ አስረዳ፤ በዚያም ዕፅ አዳም ተድላ ደስታ ካለበት ከገነት ወጣ፤ ከድንግል የተወለደ አካላዊ ቃል መስቀል ግን የድኅነት ምክንያት እንደሆነ ገለጠ፡፡ በዚያም መስቀል ቀማኛ ወንበዴ የነበረው ሰው ከአባቱ ከአዳምና ከቀደሙ አባቶች ሁሉ ጋር ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ገባ፡፡" ሃይ.አበ. ፷፯፥፫-፭
ተዋሕዶው በዘየሐጽጽ ምሳሌ ሲገለጽ፦
በድንቅ ምሥጢር እንደ ቃል እና እንደ ቀለም ተዋሐደ፡፡ በልቡና ያለ ቃል በብራና በሣሉት፣ በጻፉት ጊዜ ርቀቱን ሳይለቅ አካል ገዝቶ እንዲታይ፤ አካላዊ ቃልም ርቀቱን ሳይለቅ በተዋሕዶ ግዘፈ ሥጋን ግዘፈ አካልን ገንዘብ አደረገ። ሥጋም በቃል ገንዘቡ ረቂቅ አካለ ቃልን በተዋሕዶ ገንዘብ አድርጓልና ተዓቅቦን ሳይለቅ ረቂቅ ቃልን ገንዘብ አደረገ ብለን እናምናለን። ሃይ.አበ. ፶፫፥፲፫
እንደ ብረት እና እንደ እሳት ምሳሌ ባለ ተዋሕዶ ተዋሐደ። ቀዝቃዛ ብረት ወደ እሳት በተጣለ ጊዜ የእሳትን ገንዘብ ተቀብሎ እንዲያቃጥል፤ እሳትም በብረቱ ገንዘብ ተወስኖ በጉጠት እንዲያዝ፤ ሥጋ በቃል ገንዘብ በተዋሕዶ ሕያው መለኮት ተባለ። ቃልም በሥጋ ገንዘብ ተዳሰሰ መከራ ተቀበለ።ሃይ.ቄር. ፸፫፥፲፪፣
እንደ ነፍስ እና እንደ ሥጋ ባለ ተዋሕዶ ተዋሐደ።ግዙፍ ሥጋ ከረቂቅ ነፍስ፣ ረቂቅ ነፍስም ከግዙፍ ሥጋ ጋር ባለ መጠፋፋት በተዋሕዶ፣ በተዓቅቦ ጸንተው በአንድ አካልነት እንዲገለጹ ቃልና ሥጋም እንደ ነፍስ እና እንደ ሥጋ ባለ የተዓቅቦ ተዋሕዶ ተዋሐዱ፤ ሁለትነትም ጠፍቶ አንድ ባሕርይ አንድ አካል ሆነ። ሃይ.አበ.ቄር. ፸፫፥፲፱
እንደ ባሕር እና እንደ ርጥበት ባለ ተዋሕዶ ተገለጸ። ከውኃ የገባ ሰው የውኃውን ርጥበት ገንዘብ አድርጎ በሰፊው ባሕር እንዲገለጽበት፣ በርጥበቱ ሞላ እንዲባል፣ ርጥበተ ባሕርም በአካሉ እንዲወሰን ሥጋም ቃልን በተዋሕዶ  በተዓቅቦ ገንዘብ አድርጎ በሁሉ የመላ ሆነ። ቃልም በተዋሕዶ በሥጋው  ተዓቅቦን ሳይለቅ ምልዓቱ ሳይጠፋ ተወሰነ። አረ.መን.ድር. ፳፪
እንደ ፈትልና እንደ እሳት ባለ ተዋሕዶ ተገለጸ። እሳት በፈትል ላይ ተወስኖ፣ ፈትልም በእሳት ብርሃን መልቶ እንዲገለጽ፤ ቃል በሥጋው ተወሰነ። ሥጋም በቃልነቱ ምሉዕ በኵለሄ ተባለ። ራእ. ፲፭፥፫

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

02 Jan, 14:47


፦የቅዱሳን በዓላቸው
አንዱ፦በዕለተ ልደታቸው ይታሰባሉ።
ሁለተኛ፦በዕለተ ሞታቸው ይታሰባሉ።
ሦስተኛ፦ ልዩ ተአምር በደረጉባቸው ዕለታት ይታሰባሉ።
የወር መታሰቢያ በዓላቸው ደግሞ ከሁሉም በላይ በፍጻሜ ደግላቸው በዕለተ ሞታቸው ይታሰባል።
ከዚህ ዓለም በሥጋ ተለይቶ የመጨረሻዋን ፍትሀ እግዚአብሔርን ያላገኘ ሰው ገና ሙሽራውን ለመቀበል በመጠባበቅ ላይ ነውና።"ወዳጆች ሆይ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም።ዳሩ ግን ቢገለጥ እርሱ እንዳለ እናየዋለንና እርሱን እንድንመስል እናውቃለን።"፩.ዮሐ.፫፥፪ እንዲል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

02 Jan, 12:26


የክርስትና ትምህርት በኢትዮጵያ በማን ተሰበከ?
፩ኛ ከሰብአ ሰገል አንዱ ባዚን ሰግዶ በመመለሱ።
፪ኛ በቅዱሱ ቤተሰብእ ጉዞ በእመቤታችን መምጣት ምክንያት
፫ኛ በመልአኩ ቅዱስ ዑራኤል ተልእኮ መቀደስ መቻሏ።
፬ኛ በቅዱስ ጴጥሮስ ጉባኤ መሳተፏ።
፭ኛ በጃንደረባው ሐዋርያዊ ተልእኮ ምክንያት
፮ኛ በቅዱሳን ሐዋርያት መምጣት ምክንያት።
ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮውም ከኦሪት ወደ ወንጌል ሽግግር ነው እንጂ በትንቢት በምሳሌ እና በሲባኤ ደጅ ያልጸናችውን ክርስቶስ አልተቀበለችም። ሃይማኖት፣ትንቢት፣ሱባኤ፣ክህነት፣መንግሥት፣ትምህርት፣ሆሄ እና አኀዝ፣የነባራት ስለሆነች ትፀንስን ፀንሰት ብላ ነው የተረዳችው፡፡
ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ አረዳዷ በዚህ መልኩ ይሸጋገራል፡፡
ከካህኑ ዮአኪን እና ከንጉሡ ባዚን ጀምሮ የተሰበከው አማናዊ ትምህርተ ክርስትና በቅዱስ ቅብብሎሽ ከእኛ ዘመን ደርሷል።
የክርስትና ዋና መርሆች፦መቀበል፣መጠበቅ እና መስጠት ናቸው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

02 Jan, 12:07


"ጢሞቴዎስ ሆይ በውሸት እውቀት ከተባለ፣ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍና መከራከር እየራቅህ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ።"
1.ጢሞ.6፥20

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Jan, 05:18


ለማይፈጸም ደስታ በመከራ መመካት።
በክርስትና ዓለም ውስጥ የክርስቶስን መስቀል ተሸክሞ እንደ አቅሙ ከሕማሙ ከሞቱ መሳተፍ ግድ ነው። የክርስቶስ ወገንነታችን የሚታወቀው በዚህ ተሳትፏችን ነውና።
ይህ ተሳትፎም የሚያሳፍር አይደለም።ኋላ ዕጽፍ ድርብ ጸጋ ሁኖልን በባለቤቱ እና በቅዱሳን መላእክቱ ፊት ልንደሰትበት ነው እንጂ።
እውነተኛ ደስታ ማለትም ይሄ ነው።ከተሰጠ የማይነሣ ካደረ የማይለይ ደስታ።ስለዚህ ደስታ ሲባል አሁን የሚገጥሙንን መከራዎች በክርስቶስ መስቀል እየተረጎምን ሕማምም ሞቶችን በትዕግሥት እየተቀበልን እንመካባቸዋለን።ለማይፈጸም ደስታ በመከራ መመካት ከሀላፊው ከጊዜያዊው ደስታ በላይ የሚሆን ዘለዓለማዊ ተስፋ እንዳለን  ማሳያ ነው።
"ይህም ብቻ አይደለም ነገር ግን መከራ ትዕግሥትን እንዲያደርግ ትዕግሥትም ፈተናን ፈተናም ተስፋን እንዲያደርግ እያወቅን በመከራችን ደግሞ እንመካለን።"ሮሜ.፭፥፫-፬ እንዲል።
እንዲህ ያለውን ቃለ-ደስታ ባናስብማ ሕይወታችንን የጭንቀት ሠራዊት በወረሯት ነበር።የተስፋ ቃልን ባሰብን ቁጥር ግን በሠናያን ህሊናት እንከበባለን።
ከውኀ ዳር የተተከለች ዛፍ ያለ ልምላሜ እንደማትኖር እኛም በጸጋ ወንጌል በሕገ ወንጌል ሥር ስንኖር በሀብታት በምሥጢራት እንለመልማለን።
"ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል ሕጉንም በቀንና በሌሊት የሚያስብ ሰው በውኃ ፈሳሾች ዳር እንደ ተተከለች ፍሬዋን በየጊዜዋ እንደምትሰጥ ቅጠልዋም እንደማይረግፍ ዛፍ ይሆናል።"መዝ.፩፥፪-፫ እንዲል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Jan, 05:15


በነበር ጊዜን መጨረስ ጽድቅ አይደለም።
ብየ ነበር፣አስቤ ነበር፣ቢሆን ጥሩ ነበር፣እንዲህ መሆኑን አውቄ ቢሆንማ እንዲህ አደርግ ነበር፣ነበር..በነበር ትችት ጊዜያችን አለቀ። በነበር ጊዜን መጨረስ ጥቅሙ ምንድን ነው? ምንም።ወቃሽ ህሊናን ለማስተኛት ብቻ ይጠቅም ይሆናል።
ለነፍስም ለሥጋም የሚጠቅም ተግባርን ካልሠራንበት የነበር እድሜ ዕዳ ነው።
ነበር እያሉ መውቀስ እና ማማረር ስንፍናን እና ውሳኔ አልባነትን በራስ ላይ ማጽደቅ ነው።
ተግባር በሌለው ንግግር ነበር እያሉ ብቻ መናዘዝ የጽድቅ ትሩፋት ሊሆን አይችልም።
የአባታችን የቅዱስ ጳውሎስ ምክሩ ግን ይች ናት፦"ምክንያትን ከሚፈልጉቱ ምክንያትን እቆርጥ ዘንድ አሁን የማደርገውን ከዚህ ወዲህ ደግሞ አደርጋለሁ።"፪.ቆሮ.፲፩፥፲፪ ብሎ ምክንያተኞች እንዳያመካኙ ከተግባረ ወንጌል አለመለየቱን ነግሮናል።
ሌሊት በድንኳን ስፌት ቀን በትምህርት የተጋ ሁኖ ኑሯልና።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

01 Jan, 05:06


የገነዘብ ጦር
"፦ኃጺን ኃያል ውእቱ እሳት ይመውዖ-ብረት ኃያል ነው እሳት ግን ያሸንፈዋል።
እሳት ጽኑዕ ውእቱ ማይ ይመውዖ-እሳት ጽኑዕ ነው ውኀ ግን ያሸንፈዋል።
ማይ ጽኑዕ ውእቱ ፀሐይ ይመውዖ-ውኀ ጽኑዕ ነው ፀሐይ ታሸንፈዋለች
ፀሐይ ጽኑዕ ውእቱ ደመና ይመውዖ-ፀሐይ ጽኑዕ ነው ደመና ግን ያሸንፋታል።
ደመና ጽኑዕ ውእቱ ነፋስ ይመውዖ-ደመና ጽኑዕ ነው ነፋስ ያሸንፈዋል።
ነፋስ ጽኑዕ ውእቱ መግር ይመውዖ-ነፋስ ጽኑዕ ነው ተራራ ያሸንፈዋል።
ምድር ጽኑዕ ውእቱ አዳም ይመውዖ-ተራራ ጽኑዕ ነው አዳም ያሸንፈዋል።
አዳም ጽኑዕ ውእቱ ኃዘን ይመውዖ-አዳም ጽኑዕ ነው ኃዘን ያሸንፈዋል።
ኃዘን ጽኑዕ ውእቱ ወይን ይመውዖ-ኃዘን ጽኑዕ ነው ወይን ያሸንፈዋል
ወይን ጽኑዕ ውእቱ ንዋም ይመውዖ-ወይን ጽኑዕ ነው እንቅልፍ ያሸንፈዋል
ንዋም ጽኑዕ ውእቱ ብእሲት ትመውዖ- እንቅልፍ ጽኑዕ ነው ሴት ታሸንፈዋለሽ
ብእሲት ጽንዕት ይእቲ ንዋይ ይመውዓ-ሴት ጽንዕት ናት ንዋይ ያሸንፋታል።
ንዋይ ጽኑዕ ውእቱ ሞት ይመውዖ-ገንዘብ ጽኑዕ ነው ሞት ያሸንፈዋል።"
ከሁሉም ከሁሉም የገንዘብ ጦር ሲጥል እንጂ ሲወጋ አይታይምና መጨረሻው ሞት ነው።
በዚህ ጦር የተወጋ ሰው እንደ ይሁዳ ጌታውን ሳይቀር ያሸጠዋል።
                     መጽ.ፈላ.

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

30 Dec, 09:21


"ሰማይ ሩቅ አደራ ጥብቅ"
"ጢሞቴዎስ ሆይ በውሸት እውቀት ከተባለ፣ለዓለም ከሚመች ከከንቱ መለፍለፍና መከራከር እየራቅህ የተሰጠህን አደራ ጠብቅ።"
1.ጢሞ.6፥20
ከዋነኞቹ ተቀባዮች ጀምሮ የተሰጡን አደራዎቻችን ዓይናችን እያየ በመጥፋት ላይ ናቸው።
ጳውሎስነት እና ጢሞቴዎስነት ያስፈልጋቸዋል።የሚሰጥም ተቀብሎ የሚጠብቅም ማለት ነው።
ሃይማኖት የነጻነት የፍቅር የመስቀል ዕዳ ነው።
ዕዳውን የማያውቅ ባለ ዕዳ ግን እጅጉን መፋዘዙ አይቀርም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

29 Dec, 05:12


እንደሰው ለመኖር፦
.የሰው መሆንን ትርጉምና ምሥጢር የመጀመሪያው ትምህርት ነው።(የሚያውቅ ሰው)
እግዚአብሔር ለሰው የሰጠውን ኪዳን አስቦ የሰውነትን ክብር አውቆ በሰውነት ጠባይዕ መኖር ሲቻል ነው።(የሚኖር ሰው።)
.ከሰውነት ተፈጥሮዊ ዓላማ ላለመውረድ በመስቀላዊ ዓለም ተጋድሎ ማድረግ ሲቻል ነው።(የሚጋደል ሰው።)
• ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የምታስተምረው የነገረ
ሰብእ ትምህርት በደንብ ተገንዝቦ በአንዲት ሐዋርያዊት ጉባኤ ውስጥ ሁኖ የወይኑ ግንድ ቅርንጫፍ መሆን ሲቻል ነው።(ኅዋሰ ክርስቶስ የሆነ ሰው።)
• የሰውነት ትርጉምን አሳጥቶ እንደ እንስሳትና እንደ አራዊት ከዚያም በታች
የሚያኖር ዳርዊናዊ ቲኦሪ በሕይወት ኑሮው ሳይጠልፈው በበትረ ወንጌል መከላከል ሲቻል ነው።(የቻለ ሰው።)
• በዓለም አቀፍ ፣በሀገር አቀፍ፣በሚድያ'በሥርዓተ
ትምህርት፣በሥነ መንግሥት፣በርዕዮተ ዓለም.. የሚሰነዘሩ ክብረ ሰብእ ነክ ሴራዎችን
ወጎችን ለይቶ በእውነተኛው ሰዋዊ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት
ጸንቶ ቁሞ የተጋድሎ ዘመኑን መፈጸም ሲቻል ነው።(የቻለ ሰው።)
• ሰው የተፈጠረው ዋና ዓላማ ስሙን ለመቀደስ ክብሩን ለመውረስ ነው።ይሄንን የተፈጠርንለትን ዓላማ ባለመዘንጋት መኖር ሳቻል ነው።(የኖረ ሰው።)
.እነዚህን እና የመሳሰሉትን የሚያደርግ ሰው በትክክለኛው ሰዋዊ ሕይወት የኖረ ሰው ነው።
እንደ ቅዱሳን ሰዎች ለቅድስና የኖረ ሰው ነውና ተስፋውን አያጣም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

27 Dec, 20:48


#የመላእክት-ተልእኮ-በሰው-መዳን ያለው ድርሻ!!!
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
#እግዚአብሔር መላእክትን ሲፈጥራቸው #ለሦስት ጉዳዮች ነው፦
#አንደኛ፦የባሕርይ ክብሩን በፀጋ እንዲሳተፉ ነው፡፡
#ሁለተኛ፦ሁልጊዜም እርሱን ያለ እረፍት እንዲያመሰገኑ ነው፡፡
#ሦስተኛ ለሰው ልጅና ለፍጥረታት ሁሉ ጥበቃ ነው፡፡

#ዛሬ የመልአኩ የቅ/ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል ከመሆኑም አንጻር የሰውን ልጅ ጠብቆት እናያለን፡፡
#እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ይሁን ብሎ በልዑል ሥልጣኑ እንደፈጠረው በይሁንታ መጠበቅ ይችላል፡፡

"ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና"
ሉቃ1፥37፡፡
#ነገር ግን እግዚአብሔር የባሕርይ ጠብቆቱን መላእክት በጸጋ እንዲሣተፉትና የሰውን ልጅ እንዲጠብቁት አድርጓል፡፡የሰው ልጅ አማኒም ይሁን መናፍቅ ደግም ይሁን ክፉ ጻድቅም ይሁን ኀጥእ በመላእክት ጠብቆት ውስጥ ጸንቶ የሚኖር ነው፡፡የሰው ልጅ አይ እኔ ኦርቶዶክስ ስላልሆንኩ የመላእክት ጠብቆት አያስፈልገኝም ሊል አይችልም፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር መግቦት በሁሉም ፍጥረት ላይ ስለሆነ ነው፡፡

"በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ:የሚረግሟችሁንም መርቁ ለሚጠሏችሁም መልካም አድርጉ: ስለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ:እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሓይን ያወጣልና:በጻድቃንና በኀጢአተኛዎችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። የሚወዷ፟ችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?:: ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ?አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?፡፡እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ"
ማቴ. 5:45-48
#እግዚአብሔር ለፍጡራን የሚያደርጋቸው መግቦታቱ በሙሉ የሚከናወኑ በመላእክት ተልእኮ ነው፦
ዝናሙ፣ደመናው፣ጠሉ፣ፀሐይ፣ጨረቃ፣ከዋክብት፣ነፋሳት፣መባርቅት፣ነጎድጓት...እነዚህ ሁሉ የሚመግቡን በመላእክት ተልእኮና ሥልጣን ነው፡፡ስለዚህ ዓለም በእኒዚህ መግቦት እስካለ ድረስ መላእክትን አይጠብቁኝም ማለት እኔ ከእግዚአብሔር ጠብቆትና መግቦት እልፍም ሲል በእራሴ ዓለምነት ነው የምኖር ያሰኛል፡፡

"መላእክተ ገጽንም የሚያመሰግኑ መላእክትንም በእሳት አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በጨለማና በብርሃን አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በውርጭና በበረድ አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም፡፡በውኃ ላይ በመብረቅና በነጐድጓድ ላይ የተሾሙ መላእክትንም በነፋሳት ላይ የተሾሙ መላእከተን በቁርና በውርጭ በመጾውና በክረምት በበጋና በጸደይ በምድርና በሰማይ ባሉ ነፋሳት ሁሉ ላይ የተሾሙ መላእክትን በወንዙ ሁሉ በብርሃንና በጨለማ እግዚአብሔር በባሕርይ እውቀቱ ባዘጋጃቸው በምሽትና በመንጋት ላይ የተሾሙ መላእክትን ፈጥሮአልና። የፍጥረትን ነገር ሁሉ ጻፍ ብሎ ነገረው።
ኩፋ.2፥6-7::
"ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ዑርኤል በመብረቅ በነጐድጓድ የተሾመ ነው።በሰው ቁስል የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው፡፡ ዲያብሎስን የሚበቀለው አጋንንትንም የሚበቀላቸው ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ራጉኤል ነው።ለሰው ባደረገው በጎነት ላይ ለሕዝቡ ታዛዥ ነውና ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሚካኤል ነው።በባቦች ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ገብርኤል ነው።
ሄኖ.6:2-7::
"አንዱም አንዱም በየወገናቸው እንዳሉ አንዱም አንዱ በየዘመናቸውና በየሥልጣናቸው አንዱም አንዱም በየመውጫቸውና በየስማቸው ከኔ ጋራ ያለ መሪያቸው የሚሆን የከበረ መልአኩ ዑርኤል ባሳየኝ በየወራታቸውም ጸንተው እንዲኖሩ የሚናገር መጽሐፍ ይህ ነው።
ሄኖ.21:2::
#ስለዚህ መላእክት ለሰው ልጅ በሁለተናው የሚጠብቁት ናቸው፦
ከእሳት ሲገባ አብረው ገብተው አድነውታል፡፡ከአንበሳ አፍ አድነውታል፡፡ባሕር ከፍለውለታል፡፡ከጠላት ጋር ተዋግውለታል፡፡ትንቢት ተናግረውለታል፡፡ራዕዮችን ሕልሞችን ተርጉመውለታል፡፡የክርስቶስን ሰው መሆን አብሥረውታል፡፡የክርስቶስን ልደት አብሥረውታል፡፡በጎል አብረውት አመስገነዋል፡፡በሥደት አብረው ተሰደዋል፡፡ሚጠቱን ነግረውታል፡፡በገዳም አገልገለውታል፡፡ትንሳኤውን እርገቱን አብሥረውታል፡፡ዳግም ምጽአቱን ነግረውታል፡፡ከእስርቤት አውጥተውታል፡፡ከሰይፍ አድነውታል፡፡
አጠቃላይ መላእክት ለሰው ልጅ ለደስታውም ለመከራውም በዓለ ወጎች ናቸው፡፡ስለዚህ ሰው ከመላእክት ጠብቆት መራቅ ፈጽሞ አይችለም፡፡

"ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን??"
ዕብ.1:14::
"ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፡፡ መላእክታቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና"
ማቴ.18:10፡፡
"በዚያም ዘመን ስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል:ሕዝብም ከሆነ ዠምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል:በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል"
ትን.ዳን.12:1::
"እንሆም:የጌታ መልአክ ቀረበ በቤትም ውስጥ ብርሃን በራ:ጴጥሮስንም ጐድኑን መቶ፟ አነቃውና ፦ ፈጥነህ ተነሣ አለው።ሰንሰለቶቹም ከእጁ ወደቁ። መልአኩም፦ታጠቅና ጫማህን አግባ አለው፡ እንዲሁም አደረገ"
ሐዋ.12:7-8::
#የክርስቶስ ሰው መሆን መጸነስ፣መወለድ፡መሠደድ፡መጠመቅ ማስተማር፣ሕግ መሥራት፣መሰቀል፣መሞት፣መቀበር፡መነሳት ማረግ፣ዳግም፡መምጣት ለሰው ልጅ እንደሆነ ሁሉ የመላእክትም ጥበቃ ለሁሉም ፍጥረት ነው፡፡
ስለዚህ ከመላእክት ጠብቆት ፈጽሞ መውጣት አይቻልምና የመላእክት በዓል ማክበር ለክርስትና ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ በሙሉ ነው፡፡

✞ ቅዱስ ገብር እንደ ሠለስቱ ደቂቅ እኛንም ከሦስት ነገር ይጠበቀን፦
☞ ዳያብሎስ!!! ☞ ስስእት!!!
☞ ኃጢአት!!! ☞ ፍቀረ ንዋይ!!!
☞ ፍዳ ሞት!!! ☞ ትእቢት!!!

❖እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እንላለን!!!
             ❖አ.ዘ.ያዕቆብ፡፡
            © ጌዴዎን ዘለዓለም፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

27 Dec, 06:36


አንዱ መልአክ፦
አንዱ መልአክ መልአከ ምህረትም መልአከ መአትም ይሆናል።
፦ለኖኀ መልአከ ምህረቱ ለሰብአ ትካት መልአከ መአት ነው።ሄኖ.፲፥፩-
፦ለሎጥ መልአከ ምህረቱ ለሰብአ ሰዶም መልአከ መአት ነው።ዘፍ.፲፱፥፩-፳፭
፦ለእሥራኤል መልአከ ምህረቱ ለግብጻውያን መልአከ መአት ነው።ዘጸ.፲፬፥፲፱
፦ለሕዝቅያስ መልአከ ምህረቱ ለሰናክሬም መልአከ መአት ነው።፪ነገ.፲፱፥፴፭
፦ለሠለስቱ ደቂቅ መልአከ ምህረት ነው ለባቢሎናውያን መልአከ መአት ነው።ዳን.፫፥፳፪
፦ለጴጥሮስ መልአከ ምህረቱ ለሄሮድስ መልአከ መአት ነው።ግብ.፲፪፥፯-፳፫
እግዚአብሔርም ለጻድቃን አምላከ ምህረት ነው ለኃጥአን ደግሞ አምላከ መአት ነው።ማቴ.፳፭፥፴፫
የሰው ልጅም በምህረትም በመአትም ይገለጻል።
"መቀበል ከአምላክ መማር ከመልአክ" እንዲሉ።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

27 Dec, 06:29


"በእምነት የእሳትን ኃይል አጠፉ።"
ዕብ.፲፩፥፴፬
ያለ ሃይማኖት እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት አይቻልም።
የምናምነው፦እግዚአብሔርን ለመጥቀም ሳይሆን እኛ እንድንጠቀም ነው።
በግለሰቦች ማመን እና አለማመን እግዚአብሔር የሚጎድልበት ወይም የሚጨመርለት ነገር የለም።
በጎም ለራስ ነው ክፉም በራስ ነው።
ሦስቱ ሕፃናት በስደት ሀገር ያውም በባቢሎን ሃይማኖታቸው ገልጠው በመገኘታቸው ሥነ ፍጥረቱ ሁሉ ታዘዘላቸው።ዜናቸውም ለዘመናት ሲነገር ይኖራል። አምላካቸው እግዚአብሔር አምላከ ሠለስቱ (የሠለስቱ ደቂቅ አምላክ) ተብሎ ይጠራባቸው ዘንድ የማይፍርባቸው ሆኑ።"እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነርሱ አያፍርም።"ዕብ.፲፩፥፲፮ እንዲል።
የእሳት ግብሩ ማቃጠል ነበር።ሁሉንም ነገር ስለ እግዚአብሔር ብለው በእምነት በመተዋቸው ምክንያት የእሳት ዋዕይ ሳይቀር ገረመላቸው።
፵፱ ክንድ ይውለበለብ የነበረው የባቢሎን እሳት እንደ ማለዳ ውርጭ ሆነላቸው።
ምክንያቱም በሃይማኖት ላለ ሰው የማይቻል የለምና።
ሦስቱ ሕፃናት ሃይማኖታቸውን በልብስና በምላስ የገለጡት ሳይሆን ወጣትነት፣ፍርሀት፣ማስመሰል.. ሳይገድባቸው፦በአካላቸው ቅጣትን ሞትን ለመቀበል በመወሰናቸው ነው።
መንፈሰ ረድኤት እንጂ መንፈሰ ልደት በሌለበት ዘመን ቢሆኑም በባቢሎን ጣዖት ልቡናቸው አልተናወጠም።
ይሄውም ሊታወቅ በንጉሥ ፊት ቀርበው በተመረመሩ ጊዜ የመለሱት መልስ እጅጉን የልቡና ጽንዓት የተሞላበት ነበር።
"የምናመልከው አምላካችን ከሚነድደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል ከእጅህም ያድነናል ንጉሥ ሆይ! ነገር ግን ንጉሥ ሆይ እርሱ ባያድነን አማልክትህን እንዳናመልክ ላቆምኸውም ለወርቁ ምስል እንዳንሰግድለት እወቅ አሉት።"ዳን.፫፥፲፰።
በሞታችን እንድንጠቀምበት ወዶ ከዚህ እሳት ባያድነንም እንኳን ላቆምኸው ምስል አንሰግድም አምላካችንንም አንክድም ማለታቸው ነው።
እኔስ ይሄንን ድፍረት ለራሴ አድርጌ ሳስበው አቅም ያንሰኛል።
በምላሴ እንጂ በጣቴ ነክቸው የማላውቀው ሰማዕትነት ሩቅ ይሆንብኛል።ያልቆረጠ ያልጨከነ እኖር ባይ ህሊናን ያላስወገደ ይህችን የመስቀል ፅዋዕ መች ያገኛታል?
"አለማመኔን እርዳው።"ማር.፱፥፳፬
ቅዱሳን ሰማዕታት ስለ አንዲት ሃይማኖታቸው፦በተተከለ ግንድ፣በታበለ ገመድ፣በነደደ እሳት፣በተራቡ አራዊት፣በተሳለ ስለት፣በተሾለ ቀኖት..ልዩ ልኑ ፀዋትወ መከራ ተቀብለዋል።
እኛስ? ታሪክ የምናነበው ታሪክ እንድንሠራ ነው እንጂ የታሪክ መዝገበ ቃላት እንድንሆን አይደለም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

27 Dec, 06:24


               ይህ መልአክ፦
[  ] ፦ይህ መልአክ፦"የጌታ መልአክ ነው።"ግብ.ሐዋ.፭፥፲፱።
[  ]፦ይህ መልአክ፦መላእክት በዕለተ ፍጥረት ማን ፈጠረን ባሉ ጊዜ በያለንበት እንጽና ብሎ ያረጋጋ መልአክ ነው።አክ.ዘእሑ.መቅ.ወን.
[  ] ፦ይህ መልአክ በአሥሩ ነገድ በአርባብ ላይ እና  በ፺፺ኙ የተሾመ ከ፯ቱ ሊቃነ መላእክት አንዱ ነው።ሄኖ.፳፥፯
[  ]፦ይህ መልአክ፦አዳም ሄዋን ከገነት በወጡ ጊዜ የገነት ምግባቸውን  ያዘዘላቸው ነው።ገድ.አዳ.መቅ.ወን.
[  ]፦ይህ መልአክ፦የተስፋውን ቃል ለአዳም ለሔዋን ያበሠረ ነው።ገድ.አዳ.አክ.
[  ]፦ይህ መልአክ፦ የሶምሶንን ልደት ለማኑሄ እና ለእንትኩ የሰበከ ነው።መሳ.፲፫፥፫
[  ]፦ይህ መልአክ፦ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳነ ያወጣ መልአክ ነው።ዳን.፫፥፳፰
[  ]፦ይህ መልአክ፦የተጨነቁትን የሚያረጋጋ ያዘኑትን የሚያጽናና ነው።ዳን.፱፥፳፩
[  ]፦ይህ መልአክ ዘወትር ለምልጃ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ነው።ሉቃ.፩፥፲፱
[  ]፦ይህ መልአክ፦የተሠወረውን ምሥጢር ለነቢያት የሚገልጽ ነው።ዳን.፰፥፲፮
[  ]፦ይህ መልአክ፦ መካናት ሴቶችን በብሥራቱ ልጅ እንዲወልዱ አድርጎ ደስ ያሰኘ ነው።ሉቃ.፩፥፲፫
[  ]፦ይህ መልአክ፦በዕለተ ትስብእት እመቤታችንን ያበሠረ ነው።ሉቃ.፩፥፳፮
[  ]፦ይህ መልአክ፦በዕለተ ልደት በቤተ ልሔም ተገኝቶ የምሥራቹን ቃል ለኖሎት የነገረ ነው።ሉቃ.፪፥፱
[  ]፦ይህ መልአክ፦ ዮሴፍን በህልም የመራ ነው።ማቴ.፪፥፲፫
[  ]፦ይህ መልአክ፦ በዕለተ ዓርብ ከመስቀሉ ሥር ቁሞ ሰይፉን የመዘዘ ነው።ሃይ.አበ.፳፮፥፲፬
[  ]፦ይህ መልአክ፦የጌታን ትንሣኤ ለሴቶች ያበሠረ ነው።ማቴ.፳፰፥፭
[  ]፦ይህ መላክ ጻድቃንን በገዳም ሰማዕታትን በደም ምእመናንን በዓለም ሲያጸና ሲያጽናና የኖረ ነው።ግብ.፲፪፥፰
[  ]፦ይህ መልአክ፦በዳግም ምጽአቱ የትንሣኤ ብሥራትን ለሙታን ሰባኪ ነው።፩.ተሰ.፬፥፲፮.....
        "እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ።"ሉቃ.፩፥፲፱።
       የመልአኩን ክብር አውቀን እናክብር።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

26 Dec, 12:11


"በፊታችሁ ያለውን ተመልከቱ።"
፪.ቆሮ. ፲፥፯
ኦርቶዶክሳዊ ዓይን ሦስት ነው።
አንደኛው፦ዓይን ትናንት በታሪክ መጽሄት መመለከት ነው።
ይህ ዕይታ ከዛሬ እስከ ሥነ ፍጥረት የምናይበት ነው።
ከዚያም በላይ ዘለዓለማዊ እግዚአብሔርን በእምነት የምናይበት ዓይን ነው።
ሁለተኛው፦ዓይን ዛሬን የምናይበት ተግባራዊ ዓይን ነው።አሁን የምናደርገው ነገር ሁሉ የዕይታ ውጤት ነው።
ሦስተኛው፦ነጋዊ ዓይን ነው።ነገን ታሳቢ አድርገን ስናስብ ስናልም፣ለነገ የሚሆን ሥራ ስንሠራ..ነገን እያየን ያደረግነው ትሩፋዊ ዓይን ነው።
እነዚህ ሦስት ዕይታዎች ፈጽሞ መለያየት የለባቸውም።አንድ ጊዜ ስናይ ሁሉንም ማየት ግድ ይለናል።
ያለ ትናንት ዛሬ የለም።
ያለ ዛሬም ነገ አይኖርም።
አሁን በሕይወተ ሥጋ ያለን እኛ ነገን አስበን የተከልነውን ከእኛ በኋላ የሚነሡ ልጆቻችን ይለቅሙታል።
እኛስ አሁን የምንኖርበትን ከእኛ በፊት የነበሩ አባቶች ሰጥውን አይደል?
አሁን ያለን እኛ በዓላማ ሁነን እንደክማለን።
በእኛ ድካም፣በእኛ መከራ ከእኛ በኋላ የሚነሡ ወገኖቻችን ለምልመው ይበቅሉበታል።
ከእኛ በፊት የነበሩትም እንዲህ ደክመው አብቅለው ሰጥተውናልና።
ይህ ድካም ደግሞ የትውልድ አደራ ነው።
በዚህ ሦስት ዓይኖች የተቀበልነው መጠበቅና መስጠት ሲቻል ችግራችን ሁሉ ይስተካከላል።"ለታመኑ ሰዎች አደራ ስጥ።"፪.ጢሞ.፪፥፪እንዲል።
ለዚህ ሲባል ምክንያት ሳንሰጥ፦ የትም፣መችም፣እንዴትም በሦስቱ የህሊና መረዳቶች መጓዝ፣ትሩፋት መሥራት፣ ይጠይቀናል።
ትናንት ከሁሉ በላይ በሆነች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነት ሥር የተሠራውን ታሪካችንን፦ከዕይታ ጉድለታችን የተነሣ ከሁሉ በታች እንዳናደርገው መጠንቀቅ አርቆ አሳቢነት ነው።
እግዚአብሔርም ዓለም የሚያውቅልን ጅማሪያችንን ሳይሆን አፈጻጽማችንን ብቻ ነው
ስለሆነም መፍትሄው ትናንትን ማየት፣ዛሬን መሥራት፣ነገን ማለምና ሳይሳሳቱ መጨረስ ነው።
ዛሬን የወሰነው ትናንታችን ነው።
ነገን የሚወስነውም ዛሬያችን ነው።
ትናንት የዛሬ ዘር ነበረ፣ዛሬም ደግሞ የነገ ምርት ነው።
በዘሩ ጊዜ ከዘሩ የተሳሳተ ገበሬ ከምርቱም እየተሳሳተ ነው።
በየዘመናቱ መሳሳት ይብቃን።
"ንቁ፣በሃይማኖት ቁሙ፣ጎልምሱ፣ ጠንክሩ።"፩.ቆሮ.፲፮፥፲፫ ያለው ቃል ሁልጊዜም አይለየን።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

26 Dec, 06:54


ኅብረት እና ተግባር፦
ኅብረት እና ተግባር ለሌላቸው ሰዎች ከዛሬው የነገው ይከፋባቸዋል።
ወደ ምሥራቅ ብቻ ሳይሆን ወደ ነገም ተመልከቱ መመልከቱ ጥሩ ነው።
በሠላ ህሊናም የነገ ትውልዳችሁን እና ታሪካችሁን አንብቡ? ብንባል ምን ልንል እንችላለን?
በነገው ትውልድ እና ታሪክ ፊት እኛ ማን ነን? ብለን የትውልድ እና የታሪክ ጥያቄ እስከሞታችን ድረስ የማንረሳው ህሊናዊ ጥያቄ ያስፈልጋል።
ዛሬ በሰው ፊት ከማስመሰል እና ከማፈር በነገው ትውልድ እና ታሪክ ፊት ማፈር በጣም የከፋ ነው። የጥፋት የክፋት ተባባሪ በመሆን መሥራት ግን ግፍዐ አበውን መካድ ነው።
ከሁሉም ኪዳን የአበው ግፍዕ ይከብዳል።የአበው ግፍዕ ማለት ከዚህ አሁን ካለንበት ሰዓት ጀምሮ እስከ መጀመሪያው ሰው እስከ አቤል ድረስ ለሰው ሲሉ በቸርነት አባቶቻችን የተቀበሉት መከራ ነው።
አንድ ሰው በአበው ይጀሀለሁ? ወይም አበውን! ካለ ከአዳም እስከ አሁን ባሉት አባቶች እናቶች እየተማፀነን እንደሆነ መረሳት የለበትም።
ይሄ አበዋዊ ኪዳን በትውልድ አእምሮ ውስጥ እንደ ሸማ ተጠቅልሎ እንደ ወርቅ ተንከብልሎ የሚተላለፈው በትውልድ እና በትውፊታዊ ታሪክ ውስጥ ነው።
ምድራዊት ነገ የተዘጋጀችው ተባብረው እና አቅደው ለሚሠሩ ሰዎች ብቻ ነው።
ያለዚያ ኪዳነ አበው የሌላት ሁለተኛዋ ሲኦል ትሆናለች።
ቅዱስ መጽሐፍ፦"ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት የጠራችሁ እግዚአብሔር የታመነ ነው።ነገር ግን ወንድሞች ሆይ ሁላችሁ አንድ ንግግር እንድትናገሩ በአንድ ልብና በአንድ አሳብም የተባበራችሁ እንድትሆኑ እንጂ መለያየት በመካከላችሁ እንዳይሆን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እለምናችኋለሁ።፩.ቆሮ.፩፥፲ እንዲል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

25 Dec, 06:19


ቤተ ክርስቲያንንእየጎዱ ያሉ ፈተናዎች፦
1. ወረተኛነት
2. ትዕቢት
3.ቸልተኝነት
4. ጾታዊ ፈተና
5.ጎጠኝነት
6.ዓላማ የለሽነት
7.አስመሳይነት
8.ሀሰተኛነት እና መታመን አልባነት
9.ድንቂርና የሚለውጥ ምክርን እና ትምህርትን መሸሽ
10.ፍቅረ ንዋይና ሰካራምነት
11.ባተሌነት ውለቢስነት
12.ፍርሀት እና እወደድ ባይነት
13.የባዕድ ማደሪያ መሆን።
14.መፍትሄ ጠልነት...ጽኑዕ ጽኑዕ በሽታዎቻችን ናቸው። ስለቤተ ክርስቲያን ህልውና ሲባል በዓላማ መተው ያለብንን ሳንተው ነገን ማሰብ አስቸጋሪ ነው።
ክርስቲያን ሰው የዓላማ መናኝ ነው።
የአንድ ክርስቲያን ሀብቱ ክብሩ ኦርቶዶክሳዊ አንድነት እና የሕዝብ ፍቅር ነው።ሁሉ በዚህ ይፈጸማል።
የክርስቶሳዊ ሰው ዓላማው ከሕይወቱ የቀደመ የበለጠ ልዑል ቅዱስ ነው።
ይሄንን ሁሉ ኮተት ተሸክመን ተክበስብሰን ከመኖር ግን በክርስቶስ መስቀል ላይ ተመሥርተን ሕይወት አልባ የማስመሰል ሕይወትን ከመኖር ሞት አልባ የክርስቶስ ሞትን መምረጥ ትልቅ የሰማዕትነት ጽድቅ ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

24 Dec, 15:29


ተዘክሮ ሞት ግድ ነው?
ተዘክሮ ሞት ፍርሀት አይደለም የመንገድ ዝግጅት ነው።
የሞት ወሬኛ የለውም።
ሞት የሚባለው አሁን በዚህ አለፈ የሚለውም የለም።
በግዱ በምንተወው ዓለም ለትውልዱ የሥራ አሻራ ማስቀመጥ ግን በሁለት ዓለም መለበም ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

24 Dec, 14:58


ሰው የሚለው ስም የሚጻፈው በ"ሰ"ፊደል ነው።
ይሄውም ሰብእ ነው።
"ሰ" ከሀ ጀምሮ ሰባተኛ ፊደል ናት።
"ሰ"የሰንበት ስም ናት።
"ሰ" የአዳም ፍጹምነት የሚገለጽባት ናት።
"ሰ"ሱባኤ ፍጥረት ናት።
"ሰ"ስመ ሀብት ናት።
"ሰ"ትዕምርተ ፍጽምና ናት።
"ሰ"ስመ ሰማይ ናት።
"ሰ" በዕለታት፣በዓመታት፣በሱባኤያት፣በምሥጢራት፣በሊቃናት፣በካህናት፣በሰማያት..ትመሠጠራለች።
ሰው እንኳን አካሉ ስሙ የተመሠጠረለት ምን ያክል ድንቅ እንደሆነ መመልከት መልካም ነው።
ሰው ከ"ሰ"ወጥቶ ወደ "ሠ"ከተለወጠ የሥጋ ትርጉም ይገባበታል።
ግብራችንም እንደ ስማችን ሲሆን ድርና ማግ ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

23 Dec, 17:42


የከበሩ ሰማዕታት ምንኛ ጨክነዋል።
ክርስቶስ መስቀል ተሸክሞ የመከራ ፅዋዕን ተቀብሎ ሰዋሐዳቸው አይተው ክህደትን በሃይማኖት፣ፍርሀትን በጥብዓት፣ዓለምን በማያልፍ ዓለም ለውጠው ተዋሐዱት።
ደሙን አፍስሶ ሲዋሐደቸው አይተው ደማቸውን አፍስሰው ተወሐዱት።
በሁለንተኛ ሕይወታቸው ነገረ መስቀልን ለብሰው በመስቀል ተሰቅለው ትንሿን እድሜያቸውን ኖሩ።
ከሞታቸው በኋላም ልብሳቸውን በበጉ ደም አጥበዋልና በክብር ይገለጻሉ።
ስለዚህ ንጽሕናቸው በቅዱስ መጽሐፍ፦"ከሽማግሌዎቹም አንዱ ተመልሶ። እነዚህ ነጩን ልብስ የለበሱ እነማን ናቸው? ከወዴትስ መጡ? አለኝ።እኔም ጌታ ሆይ አንተ ታውቃለህ አልሁት። አለኝም። እነዚህ ከታላቁ መከራ የመጡ ናቸው፥ ልብሳቸውንም አጥበው በበጉ ደም አነጹ።"ራእ.፯፥፲፬ ተብሎ የተመሠከረላቸው ናቸው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

23 Dec, 17:32


ሁሉም የመዳረሻ መንገዱን ይዞ እየሄደ ነው።
ባለመናወጽ ቁሞ የሚጠብቅ ምንም ፍጡር የለም።
በዚህም የፍጡርን አቅምና መጠን እንረዳበታለኝ።
ፍጡር ሁኖ በባሕርዩ ባለማለፍ ጸንቶ መኖር የሚችል ምን ነገር አለ?
እስከ ጊዜው ድረስ ግን በመተካካት ትዕዛዝ እየተውተረተረ ተፈጥሮውን ያስቀጥላል።
መተካካተን በትክክለኛው መንገድ በማስቀጠል ትዕዛዝ ግን የተፈጥሮ እና የተከሥቶ ሀላፊነት አለብን።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

23 Dec, 12:52


ይህ ቀን ይለፍ ዝም በል።
የብዙዎች ምክር ይሄ ቀን ይለፍ ዝም በል።ዝቅ ያለ እና ዝም ያለ ነው ይህንን ቀን የሚያልፈው? ይላሉ።
ቀኑ እስሲያልፍ እድሜ ያልፋል፣ታሪክ ያልፋል፣ወገን ያልፋል፣ኦርቶዶክሳውያን ያልፋሉ፣የክርስትና አሻራዎች ያልፋሉ፣እውነት ራሷ በውሸት ተተክታ እውነት መስላ ታልፋለች፣..እና ማን በመሠከራት እውነት ላይ ነው ነገን መረዳት የምንችለው? ሲባሉ።
እንግዲህ ነገርሁህ ለአንተ ብየ ነው ይላሉ።
ያለ እውነት፣ያለ ክርስትና፣ያለ ታሪክ፣..በምድር ላይ ብዙ ዓመት ኑሮ እንጀራ ለመብላት ሲባል ብቻ ዝም ማለት አይከብድም?
በመቅለስለስ ብቻ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠርሁ ክህደትና ሃይማኖትን የምለይ ፍትሀዊ ሰው ነኝ ማለት ይቻላል?
"የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሥጋችን ይገለጥ ዘንድ ሁልጊዜ የኢየሱስን መሞት በሥጋችን ተሸክመን እንዞራለን።የኢየሱስ ሕይወት ደግሞ በሚሞት ሥጋችን ይገለጥ ዘንድ እኛ ሕያዋን የሆንን ከኢየሱስ የተነሣ ዘወትር ለሞት አልፈን እንሰጣለንና።ስለዚህ ሞቱ በእኛ ይሠራል።፪ቆሮ.፬፥፲-፲፪ ያለው ቃል እንዴት ይተረጎማል?
ፍርሀትን በመላበስ፣እውነትን በማድበስበስ፣ፊት በመቀለስ፣ከንፈር በማለስለስ፣አስመሳይነት በመላበስ የክርስትና አረዳድና ሕይወት ይገለጣል?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

23 Dec, 12:02


በምድር ላይ የማይለመድ ነገር ምን አለ?
በክርስትናችን ምክንያት በታወጀብን አንዲት ምድራዊት ሕይወትን የሚነጥቀን ሞት እንኳን ተለምዶ ተራ ልምድ ሆነ።
ከሁሉም በላይ ነውርን፣ ጥፋትን፣ ኃጢአትን፣ ሆዳምነትን፣ ማስመሰልን፣ ሸንጋይነትን፣ ዓለማ ቢስነትን፣ እውነትን መርሳትን፣ ማመቻመችን ... መለማመዳችን ነው የሚያስፈራው።
ያልለመድነው የጥፋት አይነት የት ይገኛል?
መልካሙን ጥንታዋውን ልምዳችንን እየረሳን የማይጠቅመንን ልምድ ከተላበሰነ በጣም ያስፈራል።
የጥፋት ልምድ መልካሙን ሁሉ ሳያጠፋ አይቀርም። ጥፋት ልምድ ከሆነ አጥፊነቱን ማንስ ያውቅበታል?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

23 Dec, 07:57


መከራው የመስቀል ትርጉም ነው።
የዛገ ብረት ከዝገቱ የሚነጻው በእሳት ኃይል ነው።የዛገ ህሊናም ዝገተ ስንፍናውን ወደ ትንሣኤ ህሊና የሚቀይረው በመከራ መስቀል ነው።
በመስቀል ከውር ላይ ከዝገተ ኃጢአት ከዝገተ ነፍስ ከዝገተ ትሩፋት እንላቀቃለን።
ብረት ከቅዝቃዜውም የሚግለው በእሳት ግለት ነው።እሳቱ የብረቱን ዝገቱንም ቅዝቃዜውንም ያስወግድለታል።
ወይም በእሳቱ ሙቀት ብዛት ብረቱ ይታደስበታል።
በመስቀል ሕይወት እና በፈተና ውስጥ ያለ አማኝም እንዲሁ ነው።ይበልጥ ሲፈተን ይበልጥ ይግላል።ይበልጥ ሲግል ይበልጥ ቅዝቃዜው ድንዛዜው ውዝዋዜው ይለቀዋል።
ጽኑዕ አማኝ እንደ ንሥር የሚታደረው በሕይወቱ ውስጥ በሚያገኘው የመስቀል ፈተና ነው።ህሊናውን ለተዘክሮተ መስቀል።፣እግሩን ለጠጠር ደረቱን ለጦር፣እጁን እግሩን ለተሳለ ቀኖት፣አፉን ለመራራ ሀሞት ሰጥቶ፦ሊደርስባት የፈለጋትን የተስፋ መስቀል ዓላማውን ሥዕልት ብርህት ሁና እስኪያያት ድረስ ያጋጠመውን የኋላውን ፈተና ታሪክ እና ትምህርት እያደረገ እንደ ቅዱስ ነቢይ ወደፊት እያየ እውነትን መግለጥና በርትዕ ጎዳና መጓዝ ይጠይቀዋል። ሐዋርያ ትሩፋት ቅዱስ ጳውሎስ፦"ወንድሞች ሆይ እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቈጥራለሁ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ።"ፊል.፫፥፲፫ እንዳለ።
የወርቅ ጽርየት በእሳት ግለት በመዶሻ ብዛት እንደሆነ የእውነተኛነት የመስቀል መገለጫዋም በብዙ ዓርባዊ መከራ እና ፈተና ውስጥ ነው።
ሳይሰቀሉ ክብር፣ሳይሞቱ ትንሣኤ፣ሳይነሡ ዕርገት የለምና።
አማኙ ገበሬ እንኳን የዘራው ዘር ከልበሰበሰ አይበቅልለትም።ይበልጥ ለመብቀል ዘሩ ይበልጥ ወደ ጭቃው መጣል አለበት።
ይበልጥ በጸጋ ክርስትና ውስጥ የመስቀል ዓላማን ተክሎ ለማደግ ማለፍ ያለብንን የፈተና መስቀል ጎዳና ማለፍ ግድ ይላል።
አንበጣ ከሞተበት  ቦታ ሽህ ሁኖ ይወለዳል ሐዋርያዊ፣ኦርቶዶክሳዊ፣እውነታዊ.. ዓላማ ያለው ሰውም ከዋለበት ቦታ ሽሁን ባለ መስቀል በለ ሃይማኖት ያደርጋል።ቢሞት እንኳ በዕለ ዓርብ ከመስቀሉ ሥር ብዙ ሙታን ሕያዋን ሁነው እንደተነሡ ከኖረበት ከተግባረ መስቀሉ ሥር መስለውት የሚሠሩ ይነሣሉ።በትንሣኤያቸውም ከቀደመው የበረቱ እና የጸኑ ይሆናሉ። የቀደመው መስቀላዊ ሕይወት ዘር፣ትምህርት፣ምልክት፣ጽንዓት፣ምክር፣ተግሣፅ ይሆናቸዋልና። መጽሐፍ፦"በውርደት ይዘራል በክብር ይነሣል በድካም ይዘራል በኃይል ይነሣል።"
፩.ቆሮ.፲፭፥፵፫ እንዲል።
ለጊዜው በመከራ መስቀል ማማጥ ግድ ነው።መከራው ተለውጦ በክብር መወለድ ግን አይቀሬ ነው።የወንጌል ተስፋ ከመስቀል በኋላ ባለ ትንሣኤ የተሰበከ ብሥራት ነውና።ያ ብሥራት ደግሞ "ሕያውን ከሙታን ጋራ ምን ትሹታላችሁ? ተነሥቶአል እንጂ በዚህ የለም።"ሉቃ.፳፬፥፭ እየተባለ የሚነገርለት እውነት ነው።
ኃይል መንፈሳዊት ስታድር መግነዘ መከራን ፍቱልኝ መቃብረ ፍርሀትን ክፈቱልኝ ማለት ይቀርና በሕይወት መመላለስ ይሆናል።
ስለሆነም ለምን መከራ መስቀሉ አገኘን? ለምን ፈተናው መጣብን? ማለቱ ይቀርና እንዴት የመስቀል ሕይወትን መለማመድ እንችላለን? እንዴትስ ሕማሙን ሞቱን ማለፍ እንችላለን? የሚለው የተግባር ጥያቄ ይሆናል። በደንብ ለመነሣት መከራ መስቀሉ መድኃኒታችን ነው።መከራውም የመስቀሉ ትርጉም ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

22 Dec, 17:34


ክፉውን፡ ለማለፍ ፡በጎውን፡ ለመቀበል ፡ነቢይነት፡ የዘመን፡ መሰላል፡ ነው።
፦ ቤተ ክርስቲያንም፡ ክፉ ፡ዘመንን ፡የምታልፈው፡ በነቢይነት ፡ ዐይን፡ ዕይታ ፣በሐዋርያዊ ፣አንደበት፡ በማስተማር፣ በሠማእትነት፣ ጥባት፡ መከራውን ፡በመታገሥ በክርስቶስ፡ አርአያነት፡ ማለት፣ ብርሀኑን፡ በዐይኗ ፣ መዓዛውን፡ በአፍንጫዋ ፡ቃሉን፡ በጀሮዋ ፡ስሙን ፡በአደበቷ ፍቅሩን ፡በልቡናዋ፡ ደሙን ፡በደሟ ፡ሥጋውን፡ በሥጋዋ፡ በእግሯቿ ፡አሠረ፥ እግሩን ፡ተዋሕዳ ፡ በጀርባዋ፡ መሥቀሉን ተሸካማ ፡ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

22 Dec, 13:05


ሕይወተ ነቢያት
"ስለዚህ እነሆ ነቢያትንና ጥበበኞችን ጻፎችንም ወደ እናንተ እልካለሁ ከእነርሱም ትገድላላችሁ ትሰቅሉማላችሁ፥ ከእነርሱም በምኵራባችሁ ትገርፋላችሁ ከከተማም ወደ ከተማ ታሳድዳላችሁ
ከጻድቁ ከአቤል ደም ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከ ገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ።
እውነት እላችኋለሁ ይህ ሁሉ በዚህ ትውልድ ላይ ይደርሳል።
ኢየሩሳሌም ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ነቢያትን የምትገድል ወደ እርስዋ የተላኩትንም የምትወግር ዶሮ ጫጩቶችዋን ከክንፎችዋ በታች እንደምትሰበስብ ልጆችሽን እሰበስብ ዘንድ ስንት ጊዜ ወደድሁ! አልወደዳችሁምም።"ማቴ.፳፫፥፴፬-፴፯

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

22 Dec, 08:02


ዘመነ ስብከት
እኛ ኢትዮጵያውያን ብዙ ሀብቶች አሉን ሀብቶቻችን ከእኛም ተርፈው በሌሎች ዓለማት ለሚኑሩ ሰዎች ምግብም ኩራትም ታሪክም ሁነው ይታያሉ።
ኢትዮጵያ የበረከት ጓዳ፣ የገነት ጎረቤት፣የእግዚአብሔር የምሥጢር ጓዳው፣ የአፍሪካውያን ኩራት ናት።
ይሄ ሁሉ ኩራት ግን አብዛኛው ከቤተክርስቲያናችን በተገኘው ሀብት የተነሣ ነው
ከእኒህም አንዱ ቅዲስ ያሬድ ነው።
ቅዱስ ያሬድ ለኦርቶዶክሳውያን እና ለኢትዮጵያውያን በመንፈስቅዱስ እየተቃኘ ብዙ ሀብታትን ሰጥቶናል፦ ታሪክ፣ዜማ፣ሥነ ጽሑፍ፣የድርሠት ልምድ፣ትምህርት፣ሥነ ምግባር ....
ቅዱስ ያሬድ ድርሰቱን የጀመረው ታኅሣሥ ሰባት ቀን ነው።
ቅዱስ ያሬድ በዘመኑ ዜማውን ሲያዜም የታመሙት ይፈወሱ ያዘኑት ይረጋጉ ነበረ።
ይህ ልዩ ተአምር በኢትዮጵያውያን ዘንድ ጥያቄን ፈጠረባቸው ምንድን ነው የምንሰማው? ያዘኑት ይረጋጋሉ የታመሙት ይፈውሳሉ? የሚል ጥይቄ ያነሱ ነበረ።
ይህ ጥያቄ ሲሳብ ሲሳብ ከንጉሡ ከአጼ ገብረመስቀል ደረሰ እርሳቸውም ኢትዮያዊያን በአክሱም ጽዮን እንዲሰባሰቡ አዋጅ አወጁ።
በትእዛዛቸው መሠረት ኢትዮጵያውያን ጫፍ እስከጫፍ በአክሱም ከተሙ።
ምህላው በንጉሡ አማካኝነት ታኅሣሥ አንድ ቀን በ538 ዓ ም ተጀመረ።ለቅዱስ ያሬድ ዜማው የተገለጠለት ህዳር 6ቀን ደምሮ ነው።ታኅሣሥ ሰባት ቀን ዘመነ ስብከትን ጀመረው። በዕለቱም በንጉሡ ፊት እንዲህ ብሎ አዜመ፦
"ዘበመስቀሉ ተቀነወ ወበነቢያት ተሰብከ መላእክት ወሊቃነመላእክት ሰብሕዎ ኪያሁ ንሰብክ መድኅነ -
ትርጉም በመስቀል ተቸነከረ ነቢያትም ሰበኩት መላእክትም አመሰገኑት እኛም መድኃኒት ክርስቶስን እንሰብካለን" ብሎ ሊቁ የኢትዮያውያንን ትሁት ልመና ወደእግዚአብሔር የእግዚአብሔር ቸርነት ወደኢትዮጵያውያን አደረ።
በዕለቱም መድኅነዓለም ክርስቶስ እንደተሰቀለ ሁኖ ታላላቅ ነቢያት እየሰበኩት መላእክት እያመሰገኑት በአክሱም ጽዮን ላይ ታየ።
ኢትዮጵያውያን ዛሬ ይች ቅድስት ሀገራችን ታሪክና እምነትት በዘነጉ፣ሕገ እግዚአብሔርን በማያውቁ አቅጣጫቸው የማይታወቅ ጭሶች ስትሰቃይ ማየት እጅግ በጣም ያሳፍራል።
ያለመታከት ባለቤት ሁነን ከሠራን ወደዚያ ቅዱስ ዘመን መድረስ እንችላለን።ለእኛ ከትናንት የተሻለ ምንም ነገር የለንም።
፦መሰብ፣ጉዞን ወደትናንት ማድረግ
ትናንትን በሚኮንኑ ስድ አደጎች ግራ መጋባት መታለል ነው።
የጸዋትወ ዜማ ደቀመዛሙርት በአቋቋም ቤት በዜማ ቤት በቅዳሴ ቤት በዝማሬ መዋሥዕት ቤት ያለን ወንድሞቼ ከሽምደዳም አልፈን የሊቁንም ሕይወት እናጥና ብዙዎቻችን ትኩረታችን ሽምደዳ ላይ ብቻ ሁኗል
ጉዞ ወደሕይወት
የሊቁን በረከት ያድለን
በመ/ር ስብሐት

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

22 Dec, 06:17


ብርሃን ወደ ዓለም መጣ።
"ብርሃንም ወደ ዓለም ስለ መጣ ሰዎችም ሥራቸው ክፉ ነበርና ከብርሃን ይልቅ ጨለማን ስለ ወደዱ ፍርዱ ይህ ነው።
ክፉ የሚያደርግ ሁሉ ብርሃንን ይጠላልና ሥራውም እንዳይገለጥ ወደ ብርሃን አይመጣም።
እውነትን የሚያደርግ ግን ሥራው በእግዚአብሔር ተደርጎ እንደ ሆነ ይገለጥ ዘንድ ወደ ብርሃን ይመጣል።"ዮሐ.፫፥፲፱-፳፩
በብርሃን ክርስቶስ ብርሃነ ሃይማኖትን እንለብሳለን፣
ብርሃነ ህሊናን እናገኛለን፣
ብርሃነ ምግባርን እንለማመዳለን፣
በብርሃነ መስቀል እንኖራለን፣
ብርሃነ ሕይወትን እናገኛለን፣
ወደ ብርሃናውያን ዓለማት እንገባለን።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

21 Nov, 16:21


"ወንድ ልጅን ሁሉ ወደ ወንዝ ጣሉት ዘጸ 1:22"
ይህ ዕለት(ኅዳር 12) እሥራኤላውያን በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት በሙሴ መሪነት ቀይ ባሕርን ተሻግረው ንሴብሖን የዘመሩበት የመታሰቢያ ቀን ነው
እውነተኛ መሪ ሙሴ !!!
ሙሴ ማለት የውሃ ልጅ ማለት ነው
ወንድ ሁሉ ወደወንዝ በሚጣልበት ወራት በሳጥን ተጠቅልሎ ወደባሕር ተጥሎ ከሞት የተረፈ ከጥላ ያረፈ
ስለሆነ የውሃ ልጅ ተባለ

የሙሴ ሕይወት የጀመረው
በውሃ ነው
ፈርዖን ለክፋት ወደ ውሃ ቢያስጥለውም ሙሴ ግን ወደውሃ በመጣሉ
በኋላ ዘመን ክርስቶስ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ
መከራ ተቀብሎ የሚሰጠንን ጥምቀትን እየሰበከ ነበረ።
"ከውሃ እና ከመንፈስ ያልተወለደ
ወደእግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም እንዲል " ዮሐ 3:5
ሙሴ በሕፃንነቱ ወደውሃ መጣሉ ሰዎች በሕፃንነታቸው ለመጠመቃቸው ምሳሌ
"ሕፃናት ወደእኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው እንዲል"ማቴ 19፥14
ይህ ማለት ቤተክርስቲያን የ40 የ80 ዓመት ሰው አታጠምቅም ማለት አይደለም እንዲያማ እንዳንል ማቴ 20 የወይኑ ባለቤት የጧት የሶሰት የስድስት የዘጠኝ የአስራ አንድ ሰራተኞችን ሲቀበል
ተመልክተናል። ይህ ማለት በየትኛውም የእድሜ ክልል እንደምትቀበል ማሳያ ነው

እኔን የሚገርመኝ ሰው ለሰው ባጠመደው ወጥመድ ሕይወቱ
ሲያልፍ ነው
ፈርዖን ለዕብራውያን ወንዶች ውሃን
አዘጋጅቶ ነበር ነገር ግን እስከ ሠራዊቱ ሰጠመበት
ለሕጻናት አፈር መፍጨት
በውሃ መራጨት ልማድ ነው ጨዋታ ነው
ለፈርዖን ግን ሞት ነው
በአባቶች አባባል መንገድ ቢሔዱት ቢሔዱት
ውሃ ቢቀዱት ቢቀዱት
አያልቅም ይባላል
ለፈርዖን ግን መንገዱም
ውሃውም አለቀበት።
ፈርዖን ሆይ ጥበብህ
የት አለ? ጉድጓድ ቆፍረህ እራስህ
ተቀበርህበት
እረኛው ፈርዖን ሆይ ብልሀትህ የት አለ ? በቆረጥከው ከዘራ/ጎመድ ተደበደህበት

ፈርዖን ሆይ እግዚአብሔርን አላውቀውም እስራኤልን አልለቅም
በማለትህ ሙሴ ባሕሩን ወደቀይ ደም በመለወጥ ምልክት አሳይቶህ
ነበር ልበ ደንደና በመሆንህ ሕይወትህ በቀይ ባሕር አከተመ
የመጀመሪያ ሞትን ቀማሽ አቤል
ሞትን የቀመሰው በምንጭ ውሃ ነበር
ምንም እርሱ ደግ ቢሆንም አንተም ተከተልከው
"ዘይከሪ ግበ ለቢጹ ውእቱ ይወድቅ ውስቴቱ" እንዲል አፈ ወርቅ

ፈርዖናውያን ሆይ ከፈርዖን ምን ተማራችሁ ?
ዘጠኝ መቅሰፍት አስረኛ ሞተበኵር
አስራ አንደኛ ስጥመተ ባሕር
እንደታዘዘበት ታውቃላችሁ
ፈርዖንነትን የሚያራምድ ፈርዖናዊ
ሰው ደመውዙ እኒህ ናቸው

ፈርዖን ቢኖር ሙሴዎች ግን
ባሕሩን መሻገራቸው አይቀርም
ተሻግረውም ንሴብሖ ለእግዚአብሔር ስቡሐ ዘተሰብሐ
እያሉ መዘመራቸው አይቀሬ ነው

መጨረሻ ፈርዖን እና ሙሴ የተነጋገሩት የቃል ምልልስ ደግሞ ያስደንቃል
"ፈርዖንም ከእኔ ዘንድ ሂድ ፊቴን በአየህበት ቀን ትሞታለህና ፊቴን እንዳታይ ተጠንቀቅ አለው ሙሴም እንደተናገርህ ይሁን ፊትህን እንደ ገና አላይም አለ"ዘጸ10 :29
እውነት ነው ሙሴ እና ፈርዖን እንዳይተያዩ ቀይ ባሕር ይጋርዳቸው ነበር ሙሴ በሕይወት ፈርዖን በሞት ተሸፍነው ነበር።
ይህ ሁሉ የተፈጸመው
በእግዚአብሔር ቸርነት በቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነት ነውና
እግዚአብሔር በቸርነቱ ከመልአኩ እርዳታ ያድለን አሜን።

አብርሃም ፈቃዴ

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

21 Nov, 14:51


ኦርቶዶክሳዊነት የሰውን ተፈጥሮ እኩልነት ማመን፣ ማስተማር ነው፡፡ በኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮ የሰው ልጅ በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ የተፈጠረ ነው፡፡ ቋንቋ፣ ቀለም፣ ጾታ ሰውነትን የሚለያዩ ነገሮች አይደሉም፡፡ የሰው ሁሉ ባሕርዩ ሰውነት ነው፡፡ የሰው ሁሉ ሰውነቱ የተገኘው በነፍስና ሥጋ ተዋሕዶ ነው፡፡ ኦርቶዶክሳዊነት ከተፍጥሯዊ ሰብአዊነትም ከፍ ይላል፡፡ ክርስቶስን በመምሰል ተግባራዊ ሕይወት ስናድግ ወደ መልአካዊነት እንደርሳለን፡፡ ይህም የሰውነት ባሕርያችን ሳይለወጥ የነፍሳችን ባሕርይ በሥጋችን ላይ ሲሰለጥን የመላእክትን ሕይወት ገንዘብ የማድረግ ምሥጢር ነው፡፡

ሰሎሞን ላመሰግን

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

21 Nov, 09:48


#ለደም ከተማ ወዮላት!!!
"''''''''''''''''''''''''''''''''''"""'''''''''
በሁለንተናዋ ሐሰትና ቅሚያ ሞልቶባታል፣ንጥቂያ ከርሷ አያልቅም።
ናሆም 3፥1::
#ነቢዩ ናሆም በዘመኑ የነበሩ በዐለ ጊዜዎች በግዝአታቸው የሥልጣን ርዝማኔ የሚጠቀሙት የንጹሓንን ሕይወት በመቅጠፍ ነበር፡፡ስለዚህ በንጹሓን ደም የምትሠራ ከተማ ለመፍረስ እየተገነባች እንደሆነ ነቢዩ ለደም ከተማ ወዮላት ይላል፡፡

#እግዚአብሔር የማነኛው ፍጡር ደም ሲፈስ ዝም ብሎ የሚመለከት አምላክ አይደለም ቀናተኛ መስተበቀል (ፈራጅ) አምላክ ነውና፦
"እግዚአብሔር የበቀል አምላክ ነው፡፡የበቀል አምላክ ተገለጠ፡የምድር ፈራጅ ሆይ፥ከፍ ከፍ በል፤ለትዕቢተኛዎች ፍዳቸውን ክፈላቸው"
መዝ. ዳዊ. 94:1::
"አስቀድመን ደግሞ እንዳልናችሁና እንደ መሰከርንላችሁ፥ጌታ ስለዚህ ነገር ሁሉ የሚበቀል ነውና፥ማንም በዚህ ነገር አይተላለፍ ወንድሙንም አያታል፟"
1ኛ.ተሰ. 4:6::
"በመካከልህ ያለው አምላክህ እግዚአብሔር ቀናተኛ አምላክ ነውና"
ኦሪ. ዘዳ. 6:14::

#እግዚአብሔር ቀናኢ ወመስተበቅል ሲባል ለአምልኮቱ ብቻ አይደለም በአርኣያውና በአምሳሉ የፈጠረውም የሰው ደም ሲፈስ ደም አፍሳሾቹን ይበቀላል፡፡በእግዚአብሔር አርኣያ የተፈጠረን ሰው ደም ማፍሰስ የእግዚአብሔርን ስእል እንደመቅደደድ ነው፡፡
#እግዚአብሔር ዓለምን ሁሉ የፈጠረለት ለሰው ልጅ ነው፡፡የሰው ልጅ በሰማይ በምድርም ያለው ፍጥረት ሁሉ ለእርሱ አገልግሎት የተፈጠረ ነው፡፡
#መላእክት፣ፀሐይ፣ጨረቃ፣ከዋክብት፣ደመናው፣ዝናሙ፣ጉሙ፣ሰማይ፣ምድር፣ውቅያኖስ፣እንስሳት፣አራዊት፣አእዋፍ፣አሳዎች፣መንግሥተ ሰማይ፣ገነት፣ሲኦል፣ገሀነም...ይህ ሁሉ ለሰው ብቻ የተፈጠረ ነው፡፡ሰው አጠቃላይ ከእግዚአብሔር በታች ከፍጡራን በላይ ነው፡፡

#እግዚአብሔር ሥጋ የለበሰለት ሥጋን የባሕርይ አምላክ ያደረገለት፣እግዚአብሔር መከራ የተቀበለለት፣የተሰቀለለት፡የተሰደደለት ሥጋውን የቆረሰለት፤ደሙን ያፈሰሰለት፤ሐሞት የጠጣለት የተገረፈለት፡የተቀበረለት የተነሳለት ሰው ነው፡፡ሰው ግሩም የሆነ ረቂቅ የማይመረመር መልዕልተ ኩሉ ነው፡፡
"እግዚአብሔርም አለ፦ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር፤የባሕር ዓሣዎችንና የሰማይ ወፎችን፥እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ"
ኦሪ. ዘፍ. 1:26::
" ከእናንተ አንዱ ከባልንጀራው ጋራ ሙግት ቢኖረው በቅዱሳን ፊት በመፋረድ ፋንታ በዐመፀኛዎች ፊት ሊፋረድ ይደፍራልን?ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን?በዓለምስ ላይ ብትፈርዱ ከሁሉ ይልቅ ትንሽ ስለሚሆን ነገር ልትፈርዱ አትበቁምን?የትዳር ጕዳይ ይቅርና #በመላእክት እንኳ እንድንፈርድ አታውቁምን"??
1ኛ.ቆሮ. 6:3፡፡
#እግዚአብሔር የንጹሓን ደም ሲፈስ የበጎዎችንም ደም ብቻ አይደለም፡፡በመግቦቱ ያለው ደቂቀ አዳም ሁሉ ደም በከንቱ ሲፈስ ቀናኢ ወመስተበቀል ነው፡፡እርሱ የክፋቱን ፍዳ ይፈርድበታል እንጂ ደሙ በከንቱ እንዲፈስ አይፈቅድም፡፡የንጹሓን ደም ወደ እግዚአብሔር መጮህን አያቆም ይህ የዓለም እውነታ ነው፡
ነቢዩም ለደም ከተማ ወዮላት!!!ማለቱ ደሙ ሁለጊዜም አፍሳሾቹ እስኪጠፉ ድረስ መክሰሱን ስለማያቆም ከተማዋም ስለምትፈርስ ነው፡፡

"እግዚአብሔርም አለውም ፦ ምን አደረግህ??? የወንድምህ የደሙ ድምፅ ከምድር ወደ እኔ ይጮሃል።አሁንም የወንድምህን ደም ከእጅህ ለመቀበል አፏን በከፈተች በምድር ላይ አንተ የተረገምህ ነህ"
ኦሪ.ዘፍ.4:10-11::
"ከጻድቁ ከአቤል ደም ዠምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በምድር ላይ የፈሰሰው የጻድቅ ደም ሁሉ ይደርስባችሁ ዘንድ"
ማቴ.23:35፡፡
"ይህ ነፍስ ወንድሙ ቃየል በግፍ ከገደለው ከአቤል የተለየ ነፍስ ነው ልጁ ከዚህ ዓለም እስኪጠፋ ድረስ የልጅ ልጁም ከሰው ልጅ ተለይቶ እስኪጠፋ ቃየልን ይከሳል ብሎ መለሰልኝ"
መጽ.ሄኖ. 6:28
"በግፍ የፈሰሰ የፃድቃን ደም ዋጋ ስለሰጠ የመላእክት ጌታ ስም አምነው ፈጽመው ያመሰናግሉ...የጻድቅ ባሕርይ ክርስቶስም ደም በመላአክት ጌታ ፊት ተወደደ"
መጽ.ሄኖ.12:35.40::
#አሁን አሁን እየሆነ ያለው ይህ ይመስላል በንጹሓን ደም ውብ የሆነች ከተማ መገንባት፡፡ነገር ግን ደሙ ይጮሃልና ተገንብታ ሳታልቅ ለመፍረስ እየተዘጋጀች ነው፡፡እንደ ዓለም ታሪክም የደም ከተማ ተአምር ቢፈጠር ታሪክ ሆና ትቀራለች እንጅ ሕያውት ሆና አትቀጥልም፡፡

"እግዚአብሔርም አለ፦እንሆ፥እነርሱ አንድ ወገን ናቸው፡፡ለሁሉም አንድ ቋንቋ አላቸው፤ይህንም ለማድረግ ዠመሩ፡፡አሁንም ያሰቡትን ሁሉ ለመሥራት አይከለከሉም፡፡ኑ፣እንውረድ፤አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚያ እንደባልቀው፡፡እግዚአብሔርም ከዚያ በምድር ሁሉ ላይ በተናቸው፤ከተማዪቱንም መሥራት ተዉ።ስለዚህም ስሟ ባቢሎን (የተበተነች) ተባለ፥እግዚአብሔር በዚያ የምድርን ቋንቋ ሁሉ ደባልቋልና ፤ ከዚያም እግዚአብሔር በምድር ሁሉ ላይ እነርሱን በትኗቸዋል።
ኦሪ.ዘፍ.11:6-10::
#የደም ከተማ መጨረሻዋ የባቢሎን እንጣ ፋንታ ነው!!!
#ቅዱስ ሚካኤልም ዛሬ የተበደሉትን ደም የተበቀለበት ቀን ነውና እንኳን ለመልአከ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ!!!

©ጌዴዎን ዘለዓለም፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

18 Nov, 03:54


https://t.me/mstaketsehay
ገጹን ተባብረን እናሳድገው።ሁሉችሁም ለምታውቁት አጋሩልን።ቢያንስ 10ሺህ ድረስ ለማድረስ ተባበሩን።
በፔጁ የሚጻፉ ሀሳቦች ይጠቅማሉ ካላችሁ ላልደረሰው አዳርሱ።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

18 Nov, 02:39


ምን እንሥራ?
(ከሁለት ዓመት በፊት ተለጥፎ የነበረ የተደገመ)
"የሚሠራ ሰው ከአንድ ሰይጣን ጋር ይዋጋል።
የማይሠራ ሰው ግን ከሺህ ሰይጣናት ጋራ ይዋጋል።
መከራችን የሚቀንሰውም ሆነ የሚጨምረው በተግባራችን ነው።"መፍትሄው?
#1ኛ. መማር ፦አለማወቅን ያህል አስቸጋሪነት የለም የተማረ ሰው ቢያንስ ለመካሪ አያስቸግርም።የኔታ ደጉ ዓለም ካሣ እንዲህ ይሉ ነበር፦"የተማረ ሰው እና የተገጠበ አህያ አንድ ነውደ የተገጠበ አህያ የሚጫነው እየተቁነጠነጠ ነው ።የተማረ ሰውም ቢያጠፋ እንኳን እየተጨነቀ እየተቁነጠነጠ ነው።"ብለዋል።ዕውቀት ከብዙ ችግር አርነት ታወጣለች። ሲያጠፉ እንኳን በህሊና ትገስጻለች።እውነተኛ ጥርት ያለ ኦርቶዶክሳዊ አስተምህሮን መማር ዐይነ ብዙ ያደርጋል።በቀዳማውያን አበው ዐይን ያያል፣በአበው ልብ ያስባል፣በክርስትና አስተምህሮ የግል ዕውቀት የለምና። ከጥንት በቅብብሎሽ የወረደውን በመቀበል የምናውቀው እና የምንኖረው ነው እንጂ።
#2ኛ.መረዳት፦ዕውቀት ብቻ መረዳት ከሌለው እንደ ሚሞሪ ካርድ መሆን ነው።ሚሞሪያችን ብዙ ቃላት ቢሸከምም ካልከፈቱት አይጮህም።ባልተረዳ ልብ ዕውቀት ብቻ ካልከፈቱት የማይናገር ይሆናል ።ይህ ያልሰላ ሕይወት፦ የማይበላ ሀሳብ ነው።ያልተረዳ ልብ በድንቁርና ያዳቃል።የእህል ጣዕም በጉረሮ፣ የሀሳብ ጣዕም በአእምሮ ይታወቃልና።በደንብ መረዳት ጣዕመ አእምሮ ነው።
#3ኛ.ቅድሚያ ለሃይማኖት መስጠት፦ከማንም በፊት ከማንም በላይ ለክርስትናው ቅድሚያ መስጠት ። መቅደም የማይገባቸው ሲቀድሙብን ደጋፊ እና ከዳሚ ያደርጉናል።በዐይን ሌላውን ያዩበታል እንጂ እርሱን ዐያዩትም በሃይማኖትም ሌላውን ያዩበታል ሌላውን ያውቁበታል እንጂ እርሱን አያውቁትም።ልዑል ውእቱ ዘኢይትረከብ.. እንዲል።ዐይን ጤነኛ ከሆነ የምናየው ትክክል ነው።በሃይማኖችን ማያነት ካየንበት ምሥል ሳይሆን አካል እናያለን።
#4ኛ መለኪያ ማበጀት፦መለኪያ የሌለው ሰው የውኀ ስፍር ነው። ውኀ በጠርሙስ ቢቀዱት የጠርሙስ ቅርጽ ይይዛል።በሳፋ ቢያደርጉት የሳፋ ቅርጽ ይይዛል።እንዳደረጉት ከመሆን ውጪ የራሱ ቅርጽ የለውም።ቅርጽ የለሽ እንዳደረጉት የሚፈስ ልበ ቢስ ከመሆን በላይ ምን ችግር አለ! ? ሲያሞቁን የምንግል ሲያበርዱን የምንቀዘቅ መሆን የለብንም የሚያኖረን ዓላማችን ብቻ ነው።
#5ኛ እየሆነብን ያለውን በትክክል ማወቅ፦ ትናንት የሆነብንን። ዛሬ እየተደረገብን ያለውን። ነገ ሊያደርጉብን ያቀዱትን በፈጣን አእምሮ መገንዘብ ከማን?ለምን?የት?እንዴት?መቸ?ወዘተ በሚሉ መጠይቆች ማብሰል።
#6ኛ ከእኛ እና ከእግዚአብሔር ውጪ ምንም አዳኝ ረዳት እንደሌለን መገንዘብ ፦ እየጸለይን እንሠራለን እየሠራን እንጸልያለን እንደተባለ በእግዚአብሔር ረድኤት መሥራት የምንፈልገውን ሁሉ ማድረግ።
#7ኛ ለችግራችን መፍትሄ እኛው መሆናችንን ማመን እና መተግበር፦በቁስላችን ላይ ጨው እየጨሠሩ አይዞህ እናድንኃለን የሚሉን አዳኞች አይደሉም አፋዛዦች ናቸው እንጂ።
#8ኛ ስልብ ሀሳቦችን ማስወገድ ፦ ስንሞት እንበዛለን፣እርሱ ይሁነን።ወዘተ የመሳሰሉትን።
#9ኛ ከአንድ ሰው መጀመር ፦አንድ ሰው ከተነካ የሁላችን እንደሆነ እንዳለ መውሰድ። የክፉዎቹ ተግባር በተናጠል እያደከሙ ኅብረተ ክርስትናችንን ማማሰን ስለሆነ።
#10ኛ ሊለካ ሊጨበጥ የሚችል የመፍትሄ መተግበሪያ ማስቀመጥ እና ያስቀመጥነውን መሆን።
ነገ እንዲህ ለመወያየትም ሆነ አቅጣጫ ማስቀመጥ ጊዜው ሊያልፍ ይችላል።
#11ኛ በሰው አጀንዳ ለማስታገስ እንጂ አቅምን አለማጥፋት ፦ መሆን የምንፈልገውን ለመሆን ብቻ ተግቶ መሥራት። የሚፈልጉት ብኩን ሰው እንድንሆን ስለሆነ።....

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

17 Nov, 10:49


ፍርሀት የኢአማኒነት ክፉ ደዌ ነው፡፡ ፈሪ አይጸድቅም፡፡ ይኽ ማለት ስለሚፈራ ከተሳለ ስለት፣ ከነደደ እሳት ገብቶ ስለ ክርስቶስ መመስከር አይችልም፤ ለምን ቢሉ ይፈራልና፡፡ በሰው ዘንድ ያልመሰከረለት ደግሞ በአባቱ ዘንድ አይመሰከርለትም፡፡ እናም ፍርሀት የዘለዓለም ሞት ነው፡፡ ጴጥሮስ በፍርሀት ፫ ጊዜ ክዷል፤ በጥብዐት ግን ፫ ሺሕ ሰዎችን በአንድ ቀን አሳምኖ አጥምቋል፡፡ ከፈራህ አታምንም፤ ካላመንክም አትድንም፡፡ የቤታችን ሰዎች የፍርሀት ቆፈን ተብትቦ የያዛቸው ለምንድን ነው? ስለማያምኑ ነው፡፡ የማያምን ደግሞ የዘለዓለም ሕይወት አይታየውም አያምንማ! በምድር ያለው ድልወት እየጎተተ ያዳፋዋል፡፡ ለዚህ ነው መከራችንን ያበዙት፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

17 Nov, 10:17


ቅዱስ መስቀል

ቅዱስ መስቀል ከሚዘከርባቸው ዕለታት አንዱ ኅዳር ስምንት ቀን ነው፡፡ በዚህ ዕለት ቆስጠንጢኖስ ባዶስ በሚባል ወንዝ በአልጋው ላይ ተኝቶ ሳለ ቅዱስ መስቀሉ በከዋክብት አምሳል ተመሳቅሎ አይቶታል፡፡

መስቀል አብርሀ በከዋክብት የሚያሰኘው ቅሉ ይህ ነው፡፡ በመስቀሉ ኀይሉን ይስጠን አሜን፡፡ (ስንክሳር ኅዳር ፰ ተመልከት)

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

17 Nov, 08:32


              ወንጌለ አህያ
የእኛ ጳጳሳት ምሥጢረ ቁርባን አልቆባቸው ነው የአህያ ሥጋን የሚሰብኩት?
የአህያ ሥጋን ሰብከው አብልተው ወንጌልን ለዓለም እንዳዳረሱ አስበው  ይሆን?
ግን የእነዚህ የሀሳብ ምንጩ ምንድን ነው?
የአህያ ሥጋ መበላት እና አለመበላት አሳስቧቸው ነው መግለጫ መስጠት ያስፈለጋቸው? በቤተ ክርስቲያን ህልውናማ አያገባቸውም ማለት ነው።
ሃይማኖት የሌላቸው የሃይማኖት አባቶች የሚሰብኩት እንደዚህ ነው።
እነዚህ ሰዎች ችግር ፈጣሪዎች ብቻ ሳይሆኑ ራሳቸው ችግሮች ናቸው።
  የስብከት ምንጫቸውም ወንጌለ አህያ  ሳይሆን አይቀርም።
በጣም የናቅሁትን ጻፍሁት ይቅርታ።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Nov, 17:08


አስረስ የኔሰው በቁጭት ታሪክ ሲጽፉ!

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Nov, 16:10


             
    መሞት አይቀርም እውነት ግን አትሞትም
በምድር ላይ ትክክለኛው ሀቁ ሞት እና ሕይወት ነው።
ያልኖርንበት ዘመን ኑሮ ወደ ሕይወት እንደመጣነ የምንሮርበትም ዘመን አልፎ ወደ አለመኖሮ እንሄዳለን።
ደግሞም በትንሣኤ ዘጉባኤ እንነሣለን።
ታላቁ እዳ ግን ሁለት ጊዜ መሞት ነው።
በዚህም ዓለም አሸርጋጅ፣አስመሳይ ሁኖ እውነትን ሳይመሰክሩ ከንፈራቸውን በማስመሰል ቅባት አለስልሰው ለውሸት ኑረው  መሞት ግን ዳግም ሞት ነው።
እውነትን እየተጋፉ ለውሸት እንደመኖር ያለ ድንቁርና የት ይገኛል።
የእውነተኞች እድሜያቸው አጭር ነው።
ሥራቸው ግን ብዙ ነው።
ክርስቶስ እውነትን አስተምሮ ለእውነት ሞተ፣ በታላቅ ጥበቡም ተነሣ፡፡

እስጢፋኖስም እውነትን መስክሮ ለእውነት ሞተ፣
ሐዋርያቱም፣ሰማዕታቱም፣ሊቃውንቱም እውነትን መሥክረው ለእውነት ሞቱ።
የክብር ትንሣኤን ግን ያገኛሉ።
እኛስ???
መከራ አይንካን ሆዳችን ይሙላ፣ደረታችን ይቅላ፣ምእመናንም ቢያልቁ ምን አገባን በማለት ከእውነት መጣላታችን የጤና ነው? እውነት ይሄ ነው?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Nov, 12:57


ነገን ማሰብ የሚቻለው ከጊዜያዊ ሕይወት የበለጠ ዓላማ ሲኖረን ብቻ ነው።
ከሕይወታችን ዓላማችን ሲቀድም ሕይወትንም ያስቀጥላል ሥራችን ለትውልድም ይተርፋል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Nov, 04:20


በነጠላ መልበስ እና በከንፈር ማለስለስ የሚመለስ የቤተ ክርስቲያን ችግር የለም።
እንዲያውም እግዚአብሔርንም ሰውንም ማታለል ነው።
አስመሳይነትን ያህል ኑፋቄ የለም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Nov, 03:43


"በሚሠራ ሰው ፊት የፊት አጥሮች ወይም የኋላ ገመዶች አትሁኑ" ሰይ.ነበ.

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Nov, 03:38


ጥቅም ፈላጊ ፈሪ እና አድላዊ ሰውን መሪ አድርጎ ከመሾም ወንጀልን ሕግ አድርጎ ማጽደቅ ይሻላል።
ዳግመኛም፦ጥቅም ፈላጊ ፈሪ እና አድላዊ አስመሳይ ሰውን አባት አድርጎ ከመሾም ክህደት ኑፋቄ ይቀጥል ሃይማኖት ትጥፋ ብሎ ሕግ አድርጎ ማጽደቅ ይሻላል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Nov, 03:32


በሰው ዘንድ ምስጋናን ተሸክሞ በትክክል መራመድ ለማይችል ሰው እርግማን ይሻለዋል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

15 Nov, 14:09


ቅዱሱ ቤተሰብ (እ) ከግብጽ እስከ ኢትዮጵያ

ክፍል ፪

እመቤታችን፣ ጌታችን፣ ዮሴፍና ሰሎሜ በደመና ተጭነው ጣና በደረሱ ጊዜ በደሴቷ የሚኖሩ ሰዎች በፍቅርና በክብር ተቀብለው ወደ ሀገረ ገዡ ወሰዷቸው፡፡ ሀገረ ገዡ ልጁ ታሞ ሌሊት መዝሙረ ዳዊት ሲጸልይ አንሥእ ኀይለከ ወነአ አድኅነነ አምላከ ኀያላን ርድአነ ከሚለው አንቀጽ ሲደርስ የወርቅ በትር የያዘ፣ እንደ ርግብ ሁለት ክንፎች ያሉት ቀይ ሰው በሌሊት ተገልጦ እመቤታችን ልጇ፣ ዮሴፍና ሰሎሜ ከሄሮድስ ሸሽተው እንደመጡና ሄሮድስም ብዙ ሕፃናትን እንዳስገለ ነግሮት ስለነበር በደስታ ተቀበላቸው፡፡

እንደተቀበላቸው ከየት መጣችሁ? ሲላቸው ዮሴፍ ነገሩን (የተሰደዱበትን ምክንያት) ለመሰወር እግዚአብሔር የፈጠ ረውን ምድርና ፍጥረቱን ለማየትና ለማመስገን ነው አለ፡፡ ነገር ግን ሀገረ ገዡ አስቀድሞ ከየት እንደመጡ ያውቅ ስለ ነበር እኔም ከአይሁድ ወገን ነኝ አትፍሩ በማለት ደስ አሰኝቶ አኖራቸው፡ ፡ ሀገራችን ኢትዮጵያ በቀዳማዊ ምኒሊክ ጊዜ ብሉይ ኪዳንንና ተርጉመው የሚያስተምሩ ፫፻፲፰ ሌዋውያንን ተቀብላ ስለ ነበር እንደ ሐና ነቢዪት ወለተ ፋኑኤል፣ እንደ ስምዖን አረጋዊ ያሉ ብፁዓን ሰዎች የጌታን ማዳን በተስፋ በመጠባበቅ ይኖሩ የነበሩ አበው የነበሩባት ሀገር ናት፡፡ ለዚህም ነው በአክሱም ጽዮን በኢሳ ፯፥፲፬ በጣናው ገዥ ከላይ የጠቀስነውን የጌታችንን የማዳን ሥራ የሚገልጠውን ጥቅስ ሲነገር የሰማነው፡፡

እመቤታችን ከልጇ፣ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ለ፫ ወር ከ፲ ቀን በጣና ሲቆዩ ደስ እያላቸው ነው፡፡ ታሞ የነበረው የሀገረ ገዡ ልጅም ተፈውሶለታል፡፡ በግብጽ ያገኛቸው መከራ በኢት ዮጵያ አላገኛቸውም፡፡ ግብጽ ከአሕዛባዊነት ነው ወደ ክርስ ትና የመጣቸው፡፡ ኢትዮጵያ ሀገራችን ግን ከሕገ ኦሪት ነው ክርስትናን የተቀበለችው፡፡ እናም ምሳሌው፣ ትንቢቱ፣ ሱባዔውና ተስፋው ኢትዮጵያ ሲነገር የኖረ ስለሆነ አዲስ ነገር አልነበረም፡፡ ስለዚህ የጌታችንን እናት በደስታ ነው የተቀበለች፡፡ እንደ ኮቲባ ነገረኛ፣ እንደ ሽፍቶችም አስፈ ሪ አልነበረችም፡፡ ወበሀገርነሰ አኮ ከማሁ ኢያንሶሰዋ እግረ ሐዋርያት ዲቤሃ ወኢተገብረ መንክራተ እግዚእ በውስቴታ አላ አምነቶ በዜና ወተወክፈቶ በድምጽ- በሀገራችን ግን እንዲህ አይደለም፤ የሐዋርያት እግር አልተመላለሰባትም፤ የጌታ ድንቆችም በውጧ አልተደረጉም፤ በዜና አመነችው፤ በድምጽም ተቀበለችው እንጅ እንዳለ ሊቁ፡፡ መጽሐፈ ምሥጢር ፬፥፴

ወደ ታሪኩ ስንመለስ እመቤታችን ጌቻችን፣ ዮሴፍ፣ ሰሎሜ በጣና የነበራቸው ቆይታ ከተፈጸመ በኋላ መልአኩ ዑራኤል በጥር ፲፰ ተገልጦ "ተነሣ፤ ሕፃኑን እናቱንም ይዘሂ ወደ እስራኤል አገር ሂድ" በማለት ለዮሴፍ ነገረው፡፡ ተነሥተው በደመና ሲጫኑ ሀገረ ገዡና የሀገሩ ሰዎች እያለቀሱ ተሰናብተዋቸው ወደ ቤታቸው ተመለሱ፡፡ እመቤታችን በደመና ላይ ሆነው ሲሄዱ ጎዣምን (ጎጃምን) አይታ ጌታን ስትጠይቀው ይህ ሀገር ጎዣም ይባላል፤ የዚህ ሀግ ሰዎች አስቀድመው ትስብእቴን ያምናሉ፤ ብዙ ቅዱሳንም ይኖሩ በታል ብሏት ተራሮቿን፣ ወንዞቿን ከባረከ በኋላ በደመና ተጭነው በተለያዩ የኢትይጵያ ክፍለ ሀገሮች በመዘዋወር ምድሪቱን ቀድሰዋል፡፡

በጥቅሉ፦ በሸዋ፣ በሶዶ፣ በደዋሮ፣ በሙካ፣ በኪሊሎ፣ በግንቢ፣ በሎሚ፣ በባሶ፣ በከተታ፣ በሙገር፣ በወግዳ፣ በኢፋት፣ በኤፍራታ፣ በአሰቦት፣ በጨርጨር፣ በጉራጌ፣ በከንባታ በምሁር፣ በዠንዣሮ፣ በአርሳባ፣ በቆወረራ፣ በአሞር፣ በጉራ፣ በወሎ፦ በሮሃ፣ በላታ፣ በአገው፣ በበጌምድር፣ በአምሐራ ... በሚባሉት ሀገራት በደመና ሆነው ገዳማት፣ አድባራቱ የሚታነፁባቸውን አይተውና ባረርከው በጥር ፳፱ ቀን በግብጽ በስተደቡብ በሚገኘው በቁስቋም ተራራ ላይ ዐርፈዋል፡፡ ቁስቋም ማለት መካነ ዕረፍት ማለት ነው፡፡ ከዚህ በኋላ መልአኩ ተገልጦ ለሁለተኛ ጊዜ "የሕፃኑን ነፍስ የፈለጉት ሞተዋልና ተነሣ፤ ሕፃኑንና እናቱንም ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ፤ እስክነግርህም ድረስ በዚያ ተቀመጥ" ማቴ ፪፥፴ በማለት ስለነገራቸው ወደ ሀገራቸው እስራል ተመለሱ፡፡
ምንጭ፦ ፩. ድርሳነ ዑራኤል ፪. መጽሐፈ ስንክሳር ፫. መጽሐፈ ምሥጢር ዘአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ፡፡
6/3/2017 ዓ.ም

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

15 Nov, 10:21


ቅዱሱ ቤተሰብ (እ) ከግብጽ እስከ ኢትዮጵያ

ቅዱሱ ቤተሰብ የሚባለው ቅድስትና ድንግል የምትሆን እመቤታችን ማርያም፣ ልጇ ወዳጇ ክርስቶስ፣ አገልጋዩዋ፣ ጻድቁና አረጋዊው ዮሴፍና የአክስቷ ልጅ ቅድስት ሰሎሜ ናቸው፡፡

እመቤታችን በስደቷ ወራት በግብጽ ሳለች አንበሶች መጡ ባት፡፡ ዮሴፍ ጥሏት ሲሸሽ እርሷ ልጇን ከሰሎሜ ጀርባ በመንጠቅ አዝላው ዮሳፍጥ ወደሚባል በርሃ ሮጠች፡፡ ጌታችን ግን እናቴ ሆይ! ቁሚ አንበሶች ወደ እኛ አይመጡ
ም ብሎ ካረጋጋት በኋላ አንበሶችን ገሠጻቸው፡፡ አንበሶቹ ስድስት ናቸው፤ አንዱን አንበሳ ዮሴፍን ከሸሸበት ሄደህ ና! በለው አለው፤ ዮሴፍም አንበሳውን እንደ ፈረስ ተጭኖት ተመለሰ፡፡

ከዚህ በኋላ እመቤታችን ልጇን አቅፋ፣ ዮሴፍና ሰሎሜ፣ ስድስቱ አንበሶችም በደመና ተጭነው ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ጉዞ ጀመሩ፡፡ ተጉዘውም በአንድ ቀን ናግራን ከሚባል ሀገር ደረሱ፡፡ ጌታችንም በዚህች በናግራን በኋለኛው ዘመን ስለ ስሙ ብለው ደማቸውን የሚያፈሱ ምእመናን እንደሚኖሩባት ነግሯታል፡፡ ይህም አልቀረም ኢትዮጵያዊው አጼ ካሌብ ዘምቶ ንጉሡ ፊንሐስን ድል እስኪነሣው ድረስ የደቡብ አረብ (የመን) ክርስቲያኖች በአይሁዳውያን ተጨፍጭፈው የሰማዕትነት ጸዋን ተጎንጭተዋል፡፡

ናግራንንን አይተው፣ ጌታችን ምድሪቱን ባርኮ ለእናቱ ቃል ኪዳን ከሰጣት በኋላ ከዚያ ተነሥተው ገደመ ሲሐት ደረሱ፡፡ በዚህ ቦታም ታላቅ መነኰስ እንደሚነሣ ነግሯት ሦስቱ አንበሶች በዚያው እንዲራቡ አዝዞ በሐማሴን (ኤርትራ ደብረ ቢዘን) አድርገው ደብረ ዳሞ ደረሱ፡፡ በደብረ ዳመሞ ውስጥም የቁስጥንጥንያ ንጉሥ ክብሩን ትቶ መጥቶ ከዚያ እንደሚኖርና የመላው ኢትዮጵያውያን ማረፊያ እንደሚሆን ከገለጠላት በኋላ ከደብረ ዳሞ ተነሥተው አክሱም ጽዮን ደረሱ፡፡

አክሱም ጽዮን በደረሱ ጊዜ ቤተ መቅደሱ ገብተው ሊቀ ካህናቱ አኪን ለንጉሡ ባዚን ናሁ ድንግል ትፀንስ ወትወልድ ወልደ (ኢሳ 7፥14) ያለውን ሲያነብለት ንጉሡ ድንግል በየት ነው የምትወልደው? ብሎ ሲጠይቅና ሊቀ ካህናቱም በቤተ ልሔም ዘይሁዳ እንደ ሆነ (ሚክ 5፥2 ማቴ 2፥5) ሲመልስለ ት ሰሙ፡፡ እነሱ ግን ተሰውረው ስለነበር ማንም ማን አላያቸውም ነበር፡፡ ... እስመ ጽዮን እንዘ ጽዮን አብዐለት ጽዮነ - ዮዮን (እመቤታችን) እራሱ ጽዮን ስትሆን ጽዮንን አከበረች ያሰኘው ቅሉ ይህ ነው፡፡ ከዚህ በኋላ አብረዋቸው የመጡት ሦስቱ አንበሶች በአክሱም ጽዮን አደባባይ በተገለጡ ጊዙ ንጉሡና ሠራዊቱ ደንግጠው ሲሸሹ መልአኩ ዑራኤል የትንቢቱን መድረሰና መፈጸም ነግሮ አረጋግቷቸዋል፡፡

ከአክሱም ጽዮን ወጥተው የሄዱት ወደ ደብር ዐባይ ነው፡፡ ደብረ ዐባይም ታላቅ ገዳም እንደምትሆን ነግሯት ተከዜን ተሻግረው ዋልድባ ደረሱ፡፡ በዋልድባ ጌታችን በበትረ ዮሴፍ ቆፍሮ ፫፻፲፰ ስር አወጣ፡፡ ለእናቱ ለእመቤታችንም ትበላ ዘንድ ሰጣት፤ ብትቀምሰው መረራት፡፡ ጌታችንም በኋለኛው ዘመን ይህንን እየተመገቡ፣ እንደ መዓር፣ እንደ ስኳር እየጣፈጣቸው ስምሽን የሚያመሰግኑ እልፍ አእላፍ መነኰሳት በዚህ ገዳም ይኖራሉ ብሎ ኪዳኗን አብስሯታል፡፡

ከዚህም ጋር በዚኸው ገዳም ሳሉ አንበሶች መጥተው ለእመቤታችን የፈጣሪያቸው እናት መሆኗን በመመስከር ሰግደውላታል፡፡ ከግብጽ አብረዋቸው የመጡ እነዚያ ሦስቱ አንበሶችም ከእነዚህ ጋር ወደ ጫካ እንዲገቡና በኋላኛው ዘመን ለሚነሡ ብፁዓን መነኰሳት እንደ ፈረስ እየሆኑ እንዲያገለግሏቸው በማዝ አሰናበታቸው፡፡ እነአባ ሳሙኤል ዘዋልድባ እንደ ፈሰስና ፈረሰኛ አንበሳውን ጋልበውት ይጓዙ የነበረው ከዚህ የተነሣ ነው፡፡

ከዋልድባ በደመና እየከነፉ ወደ ጣና ... በክፍል ፪ ይቀጥላል፡፡
ኅዳር 63/2017 ዓ.ም

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

12 Nov, 18:47


ቅኔ ዘረፋ

(በየኔታ መዝገበ ቃል)

ወለህ ነቅዐ ሕይወት ጉባኤ ቤት
4/3/2017 ዓ.ም

ጉባኤ ቃና

ለጉባኤ ቃና ድንግል አምጣና አምጣነ መወድስ አብ፤ አምጣነ አሐዱ ክርስቶስ ትርጓሜ እምነ ክልኤቱ ርኩብ፡፡

ከማሁ

ሐሊበ አሐቲ በግዕት ነቅዐ ሕይወት ዘወላደ መንታ ትርጓሜ፤ ለክልኤ ያጸግብ ለዝንቱ እስመ አልቦቱ ፍጻሜ፡፡

ዘአምላኪየ

ለየውሃነ ልብ ጥበብ ወአቅመ ኀልዮ ዘምክር፤
ቅሩብ እግዚአብሔር ዘመጽሐፍ ምሥጢር፤
ወመሥዋዕቱኒ የዋህ መንፈሰ ቅኔ ሥውር፡፡

ሚበዝኁ

ዘይኬልልዋ ዘልፈ ልቡሳነ መብረቅ ኪሩቤል ቁር ወአስሐትያ፤ ዘዕረፍት አልቦሙ ለድንግል ዘበአርአያ፤ መጠነ ተሰብኦት ኮነት በዘተሰብኦ ተኀጥአ ብሂለ እኅትነ ነያ፡፡

ዋዜማ

እግዚአብሔር ብሂሎትየ ከመ በድን ሥጋነ ዘእንበለ ነፍስ አሐቲ፤ መንፈስነ ዘእንበለ ፍቅር ከመ በድን ይእቲ፤ ኢይትዌ ለጥ ነፍሰ ከመ ሥጋነ መዋቲ፤ ዘእንበለ ፍቅር ነፍስ እስመ አልባቲ፤ ለነፍስነ ዘርእያ መስሐቲ፡፡

ሥላሴ

ተገልበቢ ተገልበቢ መልበሰ ጳውሎስ ተፋቅሮ ልቡና አርድእት እኅት ሀላዊተ ዛቲ ዓለም፤ ዘይበዝኅ ቁረ ተበቅሎ ዘአኮ አዳም፤ ከመ ኢይርከብኪ ቁር ተበቅሎ ሰብእ ድኩም፤ ገፋኤ ሠናያት አሥራወ ደም፤ በይነ ዓለመነ ነሥአ ዘነፋስ ጸሊም ፤ ከመ ይቤ ጳውሎስ ሐኪም፡፡

ዘይእዜ

ኦ ክርስቶስ እለ ኀቤከ ይጸርሑ ደርገ ጊዜ ተሰዶ ጸሎት፤ ረኃብ ወጽምእ ምእመናኒከ ለእምከ ይትመሐጸንዋ በኵሉ ሰዓት፤ እስከነ ታጸንን ታሕተ ክሳዳ ዘበመልዕልት፤ እስመ ለእሉ አልቦሙ ሰማዔ ስእለት፤ ብእሲ በምድር እንበለ ዛቲ ቅድስት፤ እስመ ለእሉ አልቦሙ ሰማዔ ስእለት፡፡

መወድስ

እምዘመነ አዳም ለሰብእ ዘመነ ሥጋዌ ዘዘገፋኢሁ ለሰብእ እምዘመነ አዳም መክብብ፤ እምነ ተጥብቦ ዕበድ ኢይቀርብ እግዚአብሔር ዘመነ ተድላ ዘአዳም እስከነ ይእዜ ትትገፋእ ጥበብ፤ ዘተገፍአት እምዘመኑ ለኮከበ ጽባሕ ዘኮነ ነቅዐ ሕማማት ከመ አቅራብ፤ ዘይብል ልቡናየ በሐሌ ተጥብቦ መጽብብ፤ ለእመ ጥበብ መድኃኒቱ ለአዳም ኢትትረከብ፤ ውስተ ቀያፋ ጊዜነ ዘመነ ዕበድ ዕጹብ፤ እንበለ ጥበብ ከመ ጊሜ ዘመንነ ይሰሐብ፡፡

አጭር መወድስ

ለአርድእት ሕዝብ እለ ይሴፈዉ ጸጋ፤
አስተርአየ እግዚአብሔር ቅኔየ በሥጋ፡፡

ከማሁ

ምሥጢረ ቅኔ ክርስቶስ እመ ተሰቅለ ልቡና፤
ተወልተዉ በእንተ ይእቲ ትርጓሜ ሕሊና፡፡

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

11 Nov, 02:45


         "እግዚአብሔርን ማገልገል።"
         "ከእግዚአብሔር ጋራ ማገልገል።"
አሁን አሁን የተነቃባቸው አፋዛዥ አስተማሪዎች ከሚያነሧቸው አሳቦች  እነሆ፦
"ከእግዚአብሔር ጋራ ስለማናገለግል ነው መፍትሄ ያጣነው ቅድሚያ ሕይወታችን ከእግዚአብሔር ጋራ ይሁን" ከዚያ እናገለግላለን ይላሉ።
ይሄንን ሀሳብ ስናስበው ጥሩ ይመስላል ዋና ዓላማው ግን  ችግሩ ሁሉ የገጠመን ከእግዚአብሔር ጋራ ስለማናገለግል ነው ከእርሱ ጋር አንድ እስክንሆን ድረስ አርፈን እንቀመጥ ለማለት ነው።
"አንዳንዶች እግዚአብሔር እያገለገሉ ነው መከራውን ያመጡት"ይላሉ።ይሄ ማለት አስበው አቅደው ነገን ተመልክተው የሚሠሩ ሰዎች አያስፈልጉም ማለት ነው።
ይሄንን የሚሉት የሥርዓቱ አስጠባቂ አስተማሪዎች ናቸው።ለእነሱ ትልቁ  ቁም ነገር  ማንም ሰው ያገባኛል በቤተ ክርስቲያኔ ብሎ የአቅሙን እንዳይሠራ "ከእግዚአብሔር ጋር አይደለህም አብርሆት አልደረስህም" እያሉ ማጀዘብ ነው።
የህች ሀሳብ የማናት? የጤና ናት?ለምን ተፈለገች?
እግዚአብሔር  በነጻነታችን ውስጥ ሁነን የምንሠራውን መልካም ተግባር ይባርክልናል እንጂ አይጠላውም።
ነገር ግን ገና ለገና አልበቃሁም እያለ ዝም ብሎ እንዲቀመጥ ማድረግ ግን የቀደመችው የኢየሱሳውያን ተንኮል ናት።
እነዚህ አስተማሪዎች ከእግዚአብሔር ጋራ ማገልገል የሚሉት ከሥርዓቱ ጋራ ማገልገል ለማለት መሆኑንም አንዘነጋም።
ዓይናችሁን ጨፍኑ ይታያችኋል አይነት ስብከት የተጀመረው ለዓላማ ነው።
የእግዚአብሔር ማደሪያ ለመሆንም እንሠራለን።
የእግዚአብሔር ማደሪያ ሁነንም እንሠራለን።
ጸጋ እግዚአብሔር ነገረ ድኅነት በሂደት እስከ ዕለተ ሞት ትፈጸማለችና።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

06 Nov, 05:29


              ውጦ ማላመጥ።
ክርስትና ሁሉንም ያለ አድልኦ አስፍቶ ሞልቶ አጉልቶ ያሳያል።
ከዚህ ውጪ ያለው ሌላው ደግሞ በዚሁ አንጻር አጥቦ አድልቶ ያያል።
ስሁቱ ሀሳብ ከተቃርኖ ሀሳብ በኋላ እውነትን እንደ ትልቅ ዘንዶ ይውጣታል እየዋጣትም ነው።
ለምሳሌ፦
፩_እግዚአብሔርን እና ቅዱሳኑን መምሰልን ያስተምራል----ሰይጣንን እና ሠራዊቱን መምሰልን ያስተምራል።
፪_ታሪክን ሠርቶ መጻፍና ማክበርን---ታሪክን በትርክት መቀየርና የቀረውንም መደምሠሥን
፫_አንድነትን ፍቅርን ያስተምራል ----ቡደንተኝነት ግለኝነትን መንደርተኝነትን ያስተምራል።
፬_እውነተኛነትን እና ፍትሐዊነት ማስተማር ---- ሀሰተኛነትን አድሎአዊየትና ኢፍትሐዊነት ማስተማር።
፭_ሀቀኛነትን እና ታማኝነትን ማስተማር ----ቁማርተኝነት እና ወስላታነትን ማስተማር።
ባለሀገርነትን፣ባለእሤትነትን ማስተማር----ርስት ነቃይነት፣እሴት አልባነትን ፮_ማስፈን።
፯ፈሪሐ እግዚአብሔር፣ቸርነትን ማስተማር ----ደፋር ደንቆሮነትን፣ክህደትና ህሊናቢስነት ማስተማር።
፰_ንጽሕናን፣ቅድስናን ማስተማር ----ሰዶማዊነትን፣ግብረ አራዊትን ማስተማር።
የሀገር ፍቅርን፣ለሀገር መታመንን ማስተማር--ወስላታነትን፣ባንዳነትን፣ክዳትን፣ገንጣይነትን ማስተማር።
፱_ባህልን፣እሴትን እንዲጠብቁ ማስተማር----ባህልን እሤትን እንዲንዱ ማስተማር።
፲_መከባበርን፣መተባበርን፣መፋቀርን ማስተማር----ሰውን ማዋረድን፣መለያየትን፣መጠላትን ማስተማር....በዚህ መንገድ ይቀጥላል።ይህ ተቃርኖ እንደ ዘንዶ እውነትን እየዋጣት በሀሰት እየተካት ስለሆነ ዕቅበተ እውነት ይጠይቃል።
ምክንያቱም ተቃራኒው ስሁቱ ሀሳብ ሥርዓት ሁኖ ሳያላምጥ እየዋጠን ስለሆነ።
ውጦ ማላመጥ የዘንዶ ጠባይዕ ነው።
እንስሳት በተፈጥሯቸው የተለያየ ግብር አላቸው።አላምጠው የሚበሉ የሚውጡ እንዳሉ ሁሉ በልተው ውጠው የማያላምጡም አሉ።
ታዲያ የበረሀ ሰዎች ከዘንዶው ጥርስ ለመዳን ሲባል ውጦ ሊያላምጣቸው ሲመጣ ሆዱን ይቀዱትና ይገላገሉታል።
አሁን እኛንም የገጠመን የዘንዶ ግብር የዘንዶ ሥርዓት ነው። ያውም ውጦ የሚያላምጥ ሥርዓት ።
ለዚህ ደግሞ ተውጦ  ላለመማምለጥ ሲባል በሊህ ሥሁል ዓላማን ቀርጾ ላለመዋጥ ዘንዶውን ማስተፋት አስፈላጊ ነው።
ነቢዩ ዳንኤልም የእሳት አሉሎ አጉሮሶ ነው የዘንዶውን የሆድ ጥርስ ማድቀቅ የቻለው።
የለዚያ ግን ተውጦ ከመላመጥ ያለፈ ተስፋ አይኖርም።
የአራዊት ግብር ካለው አስተሳስብ ለመዳን ሰው ሰው የሚሸት ሰዋዊ ግብርን መትከል ያስፈልጋል።
ዘግይቶ ከደረሰ እውነት ቀድሞ የደረሰ ውሸት በአእምሮ ውስጥ አድሮ መልካሙን ሁሉ ማፍረሱ አይቀርምና እውነትን አንጎትታት።
 

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

05 Nov, 12:26


የክርስትና ሃይማኖት፦
፩.ከባለቤቱ ለቅዱሳን የተገለጠ
፪.የተቀበልነው
፫.የምንብቀው
፬.የምናቀብለው ነው።
በዚህ መንገድ ከሐዋርያት እስከ ዛሬ ደርሰናል። ነገር ግን በክፉ ሥርዓት እና በስንፍናችን ምክንያት ጠባቂም ተቀባይም እያጣ ነው።
በዕቅበተ እምነት ሁኖ በሥጋ መሞት ተፈጥሯዊ ርሥት ነው።በሃይማኖት ደክሞ በነፍስ መሞት ግን ዘለዓለማዊ ደይን ነው።
ቤተ ክርስቲያን ከብዙዎቻችን ጀምሮ ተናጋሪ እንጂ ሠሪ እያጣች ነው።
በተለይም ፍርሀት እና ማስመሰል በጢሟ ሊደፏት ተቃርበዋል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

05 Nov, 11:46


አይደለም ወይ?
ያለ ተግባር ብቻውን፦ደም በማልቀስ ድንጋይ በመንከስ የቤተ ክርስቲያን ችግር አይወገድም።አውጥቶ አውርዶ ራስን ሰጥቶ ነገን ተንብዮ በመሥራት ነው እንጂ።
የዘመናት ወረቱን እንደተቀማ ነጋዴ አንገት ደፍቶ ልቡናን አሙቶ ተስፋን አጥቶ በመቆዘም ችግሩ አይፈታም።ትናንትን መሠረት አድርጎ ለነገ የሚደርስ የዓላማ የተግባር ዘርን በመዝራት ነው እንጂ።
እንዲያው ላይሆን ከንቱ እስኪሞት ድረስ እንጀራ ከመፈለግ እስኪሞቱ ድረስ የቤተ ክርስቲያንን ዕረፍት መፈለግ የተሻለው ዓላማ ነው።
ምክንያቱም መኖራችን እንኳን የሚታወቀው ለፍትህ ለእውነት እሺ ፦ለጥፋት እና ለውድመት ግን እንቢ ማለት ስንችል ነው።
ሁሉም ዘመዶች ሁሉም ወገኖቻችን የምቾን ጊዜ ጌጦች ናቸው እንጂ የፍትህ የእውነት ጊዜ ማደንዘዣዎች ማስቀየሻዎች አይደሉም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

03 Nov, 18:55


      እርዱኝ እረዳችኋለሁ     
አንድ ትልቅ አረጋዊ በረጅም የሽምግልና ዘመናቸው ጆሯቸው ሳይደነግዝ ሁሉን ይሰማሉ፣ዓይናቸው ሳይፈዝ ሁሉን ያያሉ።አንድ ሰው ይጠይቃቸዋል እንዲህ ብሎ፦"አባ እግዚአብሔር ረድቶዎት ነው እንጂ በእርስዎ እድሜ ውስጥ ያሉት እኮ ዓይናቸው ዓያይም ጆሯቸው አይሰማም?" ይላቸዋል።
እሳቸውም፦"ምን እግዚአብሔር ብቻ ይረዳኛል እኔም እግዚአብሔርን ረድቸው ነው እንጂ ወራት እየለየሁ ቅቤ እቀባለሁ፣በፀሐይ አላነብም፣ጨረር አላይም እና እኔስ እየረዳሁት አይደለምን? እግዚአብሔር የሚረዳን ስንረዳው ነው"ይሉታል።
ታዲያ በሀገራችን ብሂልም "እርዱኝ እረዳችኋለሁ ብሏል" እየተባለ ይነገራል።
ይሄንን ሀሳብ ወድጀዋለሁ እግዚአብሔር የነጻነት አምላክ ነው ወደን ፈቅደን የምናደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ይባርክልናል።የድርሻችንን ሳንወጣ ግን እርዳን ማለት ትልቅ ስንፍና ነው።
እግዚአብሔር አስገድዶ ምንም ነገር አድርጉ አይለንም። የሚጠቅመንን የሚያጸድቀንን እንድናደርግ ግን ይወዳል።
ቁጭ ብለን እግዚአብሔር ይርዳን ብንል ግን ስንፍናን በሰማይ ሰሌዳ ላይ እንደመጻፍ ነው።
"የተነቃነቀ ጥርስ ቢስቁበት አያደምቅ ቢበሉበት አያደምቅምና"ጠንክረን እንሥራ።
በሆነ ባልሆነው ነገር፦ብእል እንደበላው አቡጄዴ፣ዋግ እንደ መታው ስንዴ መሟሸሽ የወንድ ልጅ ተግባር አይደለም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

17 Oct, 19:37


ከመዝ ነአምን 
ባሕር ዳር የጠየቃችሁን :_  አዳነ የመጻሕፍት መደብር ላይ እየተሸጠ ይገኛል።

0948786851/0918719246

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

17 Oct, 05:28


ፍኖተ ሰላም ለጠየቃችሁን
መጽሐፉ ከሱቃችን ደርሷል
ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ፊት ለፊት

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

16 Oct, 03:22


      የግል ምልከታየ
ዕቅበተ እምነት ላይ እንጂ ተቋማዊ ጥበቃ ላይ ብቻ ማተኮር ማደክደክ ነው።
  ላይኛው ተቋም ለእውነት ሥራ ዝግጁ አይለም።
ከትናንት እስከ አሁን  በቤተ ክርስቲያን ላይ ለደረሰው ውስጣዊ መከራ ተቋሙ የችግር ባለቤት ሳይሆን ራሱ ችግር ነው።
በተለይም የውጭ መከራዎችን እንደ እባብ ሰይጠንን ተጭኖ እየመጣ አዳማውያንን የሚያስትበት ቤት ከሆነ ሰነባብቷል።
ህልው ሁኖ አጀንዳ የሚሰጣችሁ ማን ነው?ይሄንን የማያውቅ ሰው ይኖራል? ካላ በጣም ፈዛዛ ነው።
ይልቅስ እንደ ባለቅኔው የጥፋት መልእክቱ ደርሶና የላካችሁ ሰውየ ደኅና ነውወይ? አትሏቸውም?
ይሄንን የምጽፈው በግል ሁኖ አንዳንድ የቤቱን ተንኮል ያልተረዱ የዋሓን ምእመናን ዛሬም ሲደናገሩ በማየቴ ነው።
የማይፈወሰው ድውይ የማይመለሰው ጊጉይ ሁኖ መድኃኒቱን እያማሰነ እንደገና በደዌ እያመረቀዘ የጥፋት ቫይረስ ተሸካሚ ሁኖ ከተገለጸ ቆይቷል።
አሁንም የአትርሱኝ ጩኸት ወዲያ ወዲህ ሲያወራ ቢሰማም ምእመናንን ዕረፍት ለመንሳት፣ለማደናገር፣የንትርክ አጀንዳ ለመስጠት፣ለሥርዓቱ ጥበቃ ይጠቅማል ተብሎ የተሰጠውን የተልእኮ ዓላማ ለመፈጸም ሲባል..ነው እንጂ የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ የሚመለከተው ሁኖ አይደለም።
ይሄ ጉዳይ በደንብ ተነጋግረውበት ተወያይተውበት የአትርሱኝ አስታውሱኝ አጀንዳ እንጂ የእውነት አይደለም።ሁሉም የሚሠሩት አብረው ነው።
ዋናው ጉዳይ ምእመናንን ማደናገር፣ዕረፍት መንሳት፣እምነቱን እንዲተው ማወክ፣ሥርዓቱን መጫን፣ምእመናንን ማሳቀቅ፣ጭር ሲል አልወድም...ነው።
ቢያንስ ሞቱ እንግልቱ ይቅርና ምእመናን ሀዘናቸውን እንኳን ዕርም አውጥተው እንዳያዝኑበት ዲሪቶውን አምጥቶ ይጭንባቸዋል።
እኔ በግሌ ከነነዌ ምህላ እና ከሐምል 9/1015 ዓ.ም.ጀምሮ ጨርሸ ትቻቸዋለሁ።ረቂቅ ውንብድናውን እስከ ጥግ አይቸዋለሁ።
እኔ ግን የለውጥ መንገዱን እስካገኘው እፈልገዋለሁ።ከሕይወቴ አብልጬጬ እጨነቅለታለሁ።ሁልጊዜም ቤተ ክርስቲያን የደረሰባትን ሳስበው አንጀቴ ይላወስብኛል።
ወደ መፍትሄው ብቻ ዓይናችንን እናዙር።
የቤቱ ስም የእኛ ነው ሥራው ግን የአጥፊዎች ነው።
ሁለንተናው ኦርቶዶክሳዊ እስኪሆን ድረስ ዓይናችንን ወደ መፍትሄው ብቻ እናዙር።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

15 Oct, 21:39


         ከመዝ ነአምን፦
በዚህ አጋጣሚ እናንብብ ጉባኤ ቤቱንም የኅትመት ወጪ በመጋራት እንርዳ።ደቀ መዛሙርቱ ከ70% በላይ በዱቤ ያሳተሙትን ገዝተን በማንበብ የኅትመት ወጪ እናግዛቸው።
አዲስ አበባ
አከፋፋይ አርጋኖን መጻሕፍት መደብር፦ 0912044752፣0925421700
                   እና
ፍኖተ ሰላም
ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት፦
0913892916፣0962636489
ባሕርዳር : አዳነ መጻሕፍት መደብር

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

15 Oct, 18:13


     ከተሜው ልብህን አጽና፦      
ቀቢጸ ተስፋ የዲያብሎስ ኃጢአት ናት።
በጊዜው፣በሥርዓቱ፣በወቅቱ፣በኑሮው..ሰበብ እያደረጉ ተስፋ መቁረጥ ትልቅ በደል ነው።
ሁሉንም ነገር መቀደስ እየቻልነ ያረከስነው እኛው ነን።ሁሉም እኛ ስናከፋው ይከፋል እኛ ስንለውጠው ይለወጣል።
ጨው ኢንድንሆን ተነግሮናል።"እናንተ የምድር ጨው ናችሁ ጨው አልጫ ቢሆን ግን በምን ይጣፍጣል?"ማቴ.፭፥፲፫ ተብሎ።ታዲያ እኛው ጨው ሁነን ሟሙተን ያላጣፈጥነውን ለውጥ ከየት እናመጠዋለን?
ተስፋ ለመቁረጥ የሚያበቃን ጨው ሁነን ምን ሠርተን ነው?
የዲያብሎስ ኃጢአቱ፦ሴሰኝነት፣ሱስ፣ሆድ አይደለም።ቀቢጸ ተስፋ እና ተዕቢት ነው።በትዕቢት ላይ ቀቢጸ ተስፋ ሲጨመር ጨለማውን አስቡት።
ቀቢጸ ተስፋ፦በምድር ዓላማን ታስታለች በሰማይ ተስፋ ድኂንን ታጠፋለች።
ለምን ተስፋ እንቆርጣለን?
የምንመገበው ስላጣነ ነውን?
ሥርዓቱ ስላስጨነቀን ነውን?
ኑሮ ስለከበደን ነውን?
የምንፈልገው ውጤት ስለቀረብን?
ወይስ ከራስ ወዳድነታችን የተነሣ?
ወይስ የሞት ድምጽ ከበራችን ሁል ጊዜ ስለሚጮህብን?
ገዢዎች ሰላም ስላሳጡን?...
የምንችለውን ስለማናውቀው ወይም ስለማናደርገው ነው እንጂ በየትኛውም የሕይወት ጥያቄ አይነት ውስጥ ሁሉ ቀዳሽነታችንን ሊያሳጣን የሚችል ነገር አልነበረም።
ይሄ ሁሉ ከምን መጣ? እንዴት ልለውጠው? እንዴት ድርሻየን ልወጣ? እንዴት ጨው ልሁን? እንዴት ልቀድሰው? እንድንል ያደርጋል እንጂ ተስፋ አያስቆርጥም።
ተስፋ መቁረጥ የሚባል ደዌ በልቡናው የዞረበት ሰው ሁሉ ይጨልምበታል።ዓይኑ ጨለማ ጉልበቱ ቄጤማ ይሆናል።የሚችለው ነገር ሁሉ ያለ አይመስለውም።
ትዝ የሚለው፦ራሱን ማጥፋት፣መሰደድ፣ለተለያየ ሱስ መዳረግ፣ሰውን መጥላት፣ሥራ መፍታት፣ቁጭ ብሎ መቆዘም፣ወይም ራስን በኃጢአት መድፈቅ፣መታወክ፣መደበ፣መቀባጠር፣..የመሳሰለው የቀቢጸ ተስፋ ሠራዊቶች ሁሉ ይዘምቱበታል።
ጠላት የሚመለሰው ባጭር ታጥቆ፣ጦር ሰብቆ፣ጋሻ ነጥቆ እንደሆነ ሁሉ ወገብ ልቡናችንን በተቀደሰ ተስፋ ታጥቀን፣ዓላማን እንደ ዝናር ጠምጥመን፣ተግባርን እንደ ጦር ጨብጠን፣ ትዕግሥትን እንደ ጋሻ መክተን፣እንደ ጨው ሟሙተን፣እንደ አጃ ተፈትገን፣ቀቢጸ ተስፋን ተዋግተን ራስን ነጻ ማድረግ እና ሁሉን እንደሚገባው መለወጥ ስንችል ነው።
የቱ ይሻላል? ተስፋ ቆርጦ ዝም ማለት? ወይስ የብዙዎች ተስፋን ለመቀጠል መሥራት?
አስመሳይነታችን ለተስፋ መቁረጥ ይዳርገናል።ተስፋ መቁረጣችንም የምንኖርለትን ዓለማ ያጠፋብናል።ዓላማ የሌለው ሰው ደግም ወና በሆነ አኗኗር ውስጥ ራሱን ፈልጎ ማግኘት እና ለሌላው መትረፍ አይችልም።
ዓላማ ያለው ሰው ግን ዓማውን ከሕይወቱ አስቀድሞ ይሠራል እንጂ አይወሰልትም።
በቀቢጸ ተስፋ የተያዘ ሰው እንኳን በምድር ሊያበረክት ስለሚገባው ይቅርና ትንሣኤ ሙታን መኖሩ ያዘነጋል።
ሊቁ ዮሐንስ አፈወርቅ፦“ከመ ኢይስሀት መኑሂ በስህተተ ኃጢአት ዘውእቱ ቀቢጸ
ተስፋ ዘበአማን እምስህተተ ሰይጣን ውእቱ ወይሬስዮ ለሰብእ ከመ ይበል አልቦ ትንሣኤ ለግሙራ
ወኢ መንግሥተ ሰማያት ወኢ ኩነኔ ለግሙራ-ኃጢአት ባመጣው ቀቢጸ ተስፋ ማንም
እንዳይያዝ ይኸውም እውነተኛ ተስፋ የለም ማለት ነው። ተስፋ መቁረጥ ከሰይጣን
የተገኘ ነውና። ሰውንም ትንሣኤ ሙታን ፈጽሞ የለም መንግሥተ ሰማያትም የለም
የዘለዓለም ኩነኔ ፈጽሞ የለም እንዲል ያደርገዋል” ሃይአበ ፷፭፥፳፫ ብሎ አስተምሮናል።
  እግዚአብሔርን ዝም ብለህ መና አውርድ፣ሁሉን አስተካክል ማለት ስንፍና ነው።እየሠሩ ባርክልኝ ማለት ግን ጠቢብነት ነው።
ራስ ወዳድነት ትልቅ ሰይጣናዊት ደዌ ናት።ለዓላማ መኖር ግን የህሊና ዕረፍት ናት።ቀቢጸ ተስፋ ደግሞ የመልካም ህሊና ሁሉ ማማሰኛ ፈውሷ የራቀ ቫይረስ ናት።
ችግር ካለቀሱለት ሲያስለቅስ ይኖራል እንጂ አይገፈተርም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

15 Oct, 09:47


ዕቅበተ አእምሮ ክፍል አንድ በመ/ር መዝገበ ቃል ገ/ሕይወት
https://youtube.com/watch?v=pmBchbR_neU&si=4-UmgYLuTq8Q2Erx

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

11 Oct, 06:03


ልጅ ወደ አባቱ ይሄዳል አባትም ወደልጁ ይሄዳል!!
አባት ልጁን ይወልዳል ልጅም አባቱን ይወልዳል !!
ልጅ ያለው አባት አለው አባት ያለውም ልጅ አለው !!
ልጅ በአባቱ ይከብራል አባትም በልጁ ይከብራል !!
አባት በልጁ ነጻ ይወጣል ልጅም በአባቱ ነጻ ይወጣል !!
ልጅ በአባቱ ያጌጣል አባትም በልጁ ያጌጣል !!
ልጅ የሌለው አባት አይባልም አባት የሌለውም
ልጅ አይባልም !!
የአባት ዘሩ ልጅ ነው የልጅ ዘሩም አባት ነው !!
አባት ለልጁ በረከት ነው ልጅም ለአባቱ በረከት
ነው !!
አባት የልጁን ይወርሳል ልጅም የአባቱን ይወርሳል ።

በዚህ በችግር ወቅት አንዱም ወደ አንዱ በማይንቀሳቀስበት ወቅት
ሀገራችንም ሁለንተናዊ ችግር ውስጥ በገባችበት ዘመን የመጀመሪያ የሚጎዱ ጉባኤ ቤቶች ናቸው ።

እንደሚታወቀው ቤተክርሰቲያን የምትተነፍሰውና ሕያዊት ሆና የምትኖረው በጉባኤ ቤት ነው ።
ጉባኤ ቤት ከሌለ❖ ጵጵስናውም ❖ ምንኵስናውም ብሕትውናውም ❖ ምርጊትናውም ❖ ቅስናውም ሰባኪነቱም ❖ ዲቁናውም ❖ ክርስትናውም ❖ በጠቅላላው ምንም ነገር የሁሉም ነገር ምንጭ ቤተጉባኤ ናት ፨
ግን እንዳለመታደል ሆኖ ከላይኛው መዋቅር ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ ጉባኤ ቤቶች ይኑሩ አይኑሩ የሚያውቃቸው የለም ።
በጀትም የለም ። ድጋፍም የለም ። መምሪያም የለውም ።

በዚህ ዘመን የደቀመዛሙርቱን አዕምሮውን የሚቀልቡት መምህራን ናቸው።
ሆዱንም የሚሞሉት ከበጎ አድራጊዎች ምዕመናን ጋራ በመናበብ መምህራን ናቸው ።

ከእነዚህም መምህራን አንዱ የኔታ ገብረ መድኅን ናቸው ።
አሁንም ከአለው ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር ብዙ ነገሮች ምቹ አደሉምና በቅርብ ቀን ያሳተሙትን ከመዝ ነአምን የተሰኘ መጽሐፋቸውን ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት አሳትሞ እንዲጠቀመው አበርክተዋል ።
መጽሐፉም ወደማተሚያ ቤት ገብቶ ዛሬ ጥቅምት ሠላሳ ታትሞ ወጥቷል ከነገ ጀምሮ በጉባኤ ቤቱ አከፋፋይነት በሁሉም ከተማዎች ተደራሽ ይሆናል
ስለዚህም ኦርቶዶክሳውያን ሁላችሁም ይህንን መጽሐፍ በመግዛት ጉባኤ ቤታችሁን አግዙ ።

ጉባኤ ቤትን መርዳት እራስን መርዳት ነውና
ጉባኤ ቤትን ማገዝ እራስን ማገዝ ነውና
ጉባኤ ቤትን መጠበቅ ሀገርን መጠበቅ ነውና
ጉባኤ ቤትን መደገፍ ወላጅ አባትን መደገፍ ነውና

ጉባኤ ቤት
ጤናማ ጳጳስን
ጤናማ መነኵሴን
ጤናማ ካህንን (የነፍስ አባት)
ጤናማ ዲያቆንን
ጤናማ ሰባኪን
ጤናማ አገልጋይን የምታመርት ሐዋርያዊት እርሻ ናት ።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

10 Oct, 11:49


   አስመሳይነት ምንፍቅና ነው።
ሃይማኖት ያለው ሰው በሕይወቱ ሁሉ የሚመስለው ክርስቶስን እና የክርስቶስ ወዳጆቹን ቅዱሳንን ነው።
መድኅን ክርስቶስም በመዋዕለ ሥጋዌው መስሎ ኗሪ አልነበረም አይደለም።በአርዓያነት ግብር ሁኖ"እኔን ምሰሉ ብሎ አፋን ለመራራ ሐሞት፣ጀርባውን ለግርፋት፣እጁን እግሩን ለተሳለ ቀኖት ሰጥቶ፣አድርጎ ነው ያሳየን።
ወዳጆቹ ቅዱሳኑም ሰውነታቸውን ለተሳለ ስለት፣ለነደደ እሳት፣ለተራቡ አራዊት፣ሰጥተው፣ ዓለምን በዓለም ለውጠው፣ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ አስገዝተው፣መሆን ያለባቸውን ሁነው በተግባር መስቀሉን ተሸክመው ነው ያሳዩን።
መስሎ አዳሪ ሁኖ ጸጋን አግኝቶ ቅዱስ የተባለ ጻድቅ ፈጽሞ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የለም።ዘመን የወለደውን ንጉሥ የወደደውን ልምሰል ያለዚያማ ይህን ብሰጥ ምን እውጥ፣አንዱን ቢያሳጡኝ ወዴት እቀላውጥ ብሎ ሃይማኖተ ወንጌልን በተግባ የገለጣት የለም።
መስሎ መኖር፣መስሎ ማለፍ የመጣው ትንሣኤ ሙታንን ካለማመን የተነሣ ነው።
የሚያምኑት ግን የማይኖሩበት ትምህርት የጥቅስ መዝገበቃላት ለመሆን ብቻ ነው።
ስለሆነም መስሎ መኖር ለስላሳ ኑፋቄ ነው።
የሰው ልጅ መመሪያው ወይ እውነት ወይ ሀሰት ወይ ነው ወይ አይደለም ነው።
• ከእውነት እና ከሀሰት መካከል ምን አለ?
• ከነው እና አይደለም መካከል ምን አለ?
• ከሲኦል እና ከገነት መካከል ምን አለ?
• ከቤልሆርና ከክርስቶስ መካከል ምን አለ?
• ከዳጎን እና ከጽዮን መካከል ምን አለ?
• መልአክና ከሰይጣን መካከል ምን አለ?
ስለሆነም አስመሳይነት መካከለኛነት ነው።ከገነት ከወጡም ሲኦል ነው።ከሲኦል ከወጡም ገነት ነው።በመካከሉ ግን ለአስመሳዮት የሚሆን ቦታ የለም።ማስመሰል በክርስቶስ መስቀል ማታለል ነው።ይሄ ደግሞ ኑፋቄ ነው።"ነገር ግን ክፉዎች ሰዎችና አታላዮች እያሳቱና እየሳቱ፥ በክፋት እየባሱ ይሄዳሉ።"፪.ጢሞ.፫፥፲፫ ብሎ አባታችን እንደነገረን።
መስለህ ኑር የክርስቲያን ሀሳብ አይደለችም።ቅዱስ ጊዮርጊስ በ፸ ነገሥት መካከል ማስመሰል አቅቶት ነው በ፳ ዓመቱ "እኔ ክርስቲያን ነኝ"ብሎ ወደ ሰማዕትነት የገባው? አይደለም መሆንን ስላለበት ነው።
እስኪ እናስብ በአስመሳይነት ውስጥ ይሄ ቃል እንዴት ሊተረጎም ይችላል?፦"ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየናል? መከራ፣ወይስ ጭንቀት፣ ወይስ ስደት፣ ወይስ ራብ፣ ወይስ ራቁትነት፣ወይስ ፍርሃት፣ ወይስ ሰይፍ ነውን?"ሮሜ.፰፥፴፭ ያለው ቃል  እንዴት ይታለፋል? በፍጹም ቃሉን መሸወድ አይቻልም።መላክእትም፣ነቢያትም፣ሐዋርያትም፣ሰማዕታትም፣ጻድቃንም፣ቅ.ሊቃውንትም የኖሩት ያሉት አስመስለው ሳይሆን ሁነው ነው።
በአስመሳይነት ውስጥ ያለ ልቡና ክርስቶስን እና የእርሱ የሆኑትን ሳይቀር ለመሸወድ መሞከሩ አይቀሬ ነው።አስመሳይነት በሃይማኖተ ወንጌል፣በቅዱሳን ተጋድሎ ላይ፣ላይ መቀለድ ነው።
ዘጠና ዘጠኝ ዓመት ያለ ዓላማ በአስመሳይነት በማታለል ኑሮ እህል ጨርሶ ከመሞት አንድ ሳምንት ለዓላማ፣ለእውነት፣ለሃይማኖተ ወንጌል ኑሮ ማለፍ
ይሻላል።ቅዱስ ቂርቆስ ሦስት ዓመቱ ቢሆንም ክብሩ ግን ገናና ነው።በዕድሜኮ ብዙዎች እንበልጠዋለን።ሁሉም ሰው በእግዚአብሔር ፊት እኩል የተጠራ ነው።ጥሪውን አክብሮ መገኘት ግን ነጻ ፈቃድ ነው።
ስለሆነም የክርስትና ምሥክርነት በመኖር እንጂ በማስመሰል አይፈጸምም።"በሰው ፊት ለሚመሠክርልኝ ሁሉ እኔ ደግሞ በሰማያት ባለው በአባቴ ፊት እመሠክርለታለሁ።"ማቴ.፲፥፴፪ እንዲል።
በማስመሰል ግን ምሥክርነት የለም አይገኝም።አባታችን ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ብቻውን ሁኖ ጉባኤውን ብዙኃኑን ምሰል ሲባል ብቻየን ከእውነት ጋራ እቆማለሁ ብሎ ነው ተዋሕዶን ያስቀጠላት።
የምንናገረውንና የምናምነው ማስመሰል ሳይሆን በሕይወት እንኖረው ዘንድ አምላከ ቅዱሳን ይርዳን።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

09 Oct, 16:04


      ቁርጥ ህሊና
ሃይማኖተ ወንጌል ቁርጥ ህሊናን ትሻለች።ወጪ ወራጅ በሆነ ፈቃድ ፈጽማ አትሠራም።ቁርጥ ህሊና የሚመጣው በዓለመ መንግሥተ ሰማያት ከሚያገኘው ተስፋ የተነሣ ነው።
ከእግዚአብሔር የተረገረን ተስፋ የማያሳፍር እስከሆነ ድረስ በቁርጥ ፈቃድ ህሊናን በተስፋው ሰቅሎ ለመኖር ያበቃል።
መድኅነ ዓለም ክርስቶስ በፈቃዱ በመስቀል ተሰቅሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው እንደለያት በቁርጥ ህሊናም ወጪ ወራጅ ህሊናን በቁርጥ ተስፋ እንለይባታለን።"የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።"ገላ.፭፥፳፬ብሎ ፍጹም ሐዋርያ እንደነገረን።
ቁርጥ ህሊና የመስቀል ሕይወት ልምምድ ነው።
ወይም ለባሴ መስቀል ሁነው በሕይወተ ወንጌል ሲመላለሱ የሚገኝ ጸጋ ነው።
በቅድስት ጥምቀት እና በጥሙቅነት አኗኗር ክርስቶስን ስንለብሰው ስንመስለው በበጎ ፈቃድ ላይ ቁርጥ ህሊና ትጸናለች፦ "ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋል።"ገላ.፫፥፳፯ ብሎ ለባሴ ክርስቶስ ሐዋርያው እንደአስተማረን።
ክርስቶስን የለበሰ ሰው ሌላ የበለጠ ምድራዊ ነገር ኑሮ ቁርጥ መስቀላዊት ህሊናውን አያውከውም።
በተቀደሰቸው ርትዕት ቁርጥ ሀልዮ ውስጥ፦
ተዘክሮተ እግዚአብሔር፣
ተዘክሮተ መስቀል፣
ተዘክሮተ ሞት፣
ተዘክሮተ ትንሣኤ፣
ተዘክሮተ ፍትህ ርትዕ
ተዘክሮተ ተስፋ መንግሥተ ሰማያት ትገኛለች።
ፍትህ ርትዕት የትሩፋት ሁሉ ማከናወኚያ የቁርጽ ህሊና መዳረሻ ናት።
ነፋስ ከአፋፍ ፣ነገር ከአፍ እንደ ማይጠፋ ከርትዕት ሀልዮም ቁርጥ ህሊና አይጠፋም።
ህውኩ ልቡና ግን ከጸጋ እግዚአብሔር ይርቃል።"ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው።"ያዕ.፩፥፯ ብሎ አባታችን ያዕቆብ እንዳስተማረን።
"ማመን ከሆድ መታጠብ ከክንድ" የሚባለውም ለዚያ ነው።
የአፉ ሌላ የልቡ ሌላ ያልሆነ በቁርጥ ፈቃድ እና በመስቀላዊት ህሊና የተሰቀለ ሰው ወንጌል ዕውቀት ሳይሆን ሕይወት የሆነችው ሰው ነው።
በዚህ መንገድ ሃይማኖተ ወንጌል ዕውቀት ብቻ ሳይሆን ሕይወትም ሁና በሕይወተ መስቀል ስታኖረን ቁርጥ ህሊና ይጸናልናል።
በምድር በተናቀ ሕይወት በሰማይ በከበረ ጸጋ ለመኖር ቁርጥ ህሊና ያስፈልጋል።
ነቢይ በመዝሙሩ፦"ልቤ ጨካኝ ነው አቤቱ ልቤ ጨካኝ ነው እቀኛለሁ እዘምራለሁ።"መዝ.፶፮፥፯ ያለው በቁርጥ ህሊና ውስጥ ሁኖ ስለሚፈጽመው አምልኮት ነው።ልቤ ጨካኝ ነው ማለቱ ማንም ምንም ከቁርጥ ህሊናየ አያወጣኝም አያናወጠኝም ማለቱ ነው።
በመስቀል ለመኖር መችም፣የትም፣እንዴትም ቁርጥ ህሊና ያስፈልጋል።
በወንጌል ምድር ላይ የተተከለ ጹኑዕ ፈቃድ፣በቀራንዮ መስቀል ላይ የተሰቀለ ቁርጥ ህሊና የክብር ፍሬን ያፈራል።"ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራችኋል።"ዮሐ.፲፭፥፰ እንዲል።
      ፍሬ ሥጋ በሞት ይነሣል።ፍሬ ወንጌል ግን በትንሣኤ ዘጉባኤ እጽፍ ድርብ ሁኖ ይመለሳል።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

08 Oct, 16:22


                   ቅዱሱ ቤተሰብ
በሄሮድስ ምክንያት ለስደት የተዳረገው ቅዱሱ ቤተሰብ ተብሎ በታሪክ ፊት ይጠራል።
የቅዱሱ ቤተሰብ ዝርዝር ቅድስት እመቤታችን፣ጌታችን፣አረጋዊ ዮሴፍና ቅድስት ሰሎሜ ናቸው።
ቅዱሱ ቤተ ሰብ ወደ ግብፅ ተሰዶ ከኖረ በኋላ በፍጻሜው ወደ ኢትዮጵያም በእንግድነት መጥቷል።
ቅዱሱን  ቤተ ሰብ  በእንግድነት የተቀበለች ሀገራችንም በኪደተ እግራቸው ያገኘችው በረከት ቀላል አይደለም።
የሥርዓት ባለቤት የሆነችው ቤተክርስቲያናችንም የቅዱሱን ቤተሰብ መታሰቢያ ከክረምቱ መውጣት ጋራ አያይዛ ከመስከረም ፳፮-ኅዳር፮ ይሁን ብላ ሥርዓት ሠርታለች።ወርሑም ወርሐ ጽጌ ይባላል።
ጥንተ ስደት ግንቦት ፳፬  ነበር የ ሦስት ዓመት ከመንፈቅ የስደት ታሪክን ለመዘከር ቀናቶች ስለማይበቁ ከዓመቱ መግቢያ ከጽጌው ወቅት ጀምሮ እንዲታሰብ ሁኗል።
ይሄንን በመሰለ መልኩ በሌሎችም በዓላት ላይ ውሳኔ አሳልፋለች።ለምሳሌ፦ቃና ዘገሊላ በየካቲት ወር ነበር የውኀ በዓል ከውኀ ጥግ ብላ ከጥምቀት አስጠግታ ወደ ጥር ፲፪ አምጥታዋለች።
እንዲሁም፦በጽጌ የተመሰለች የእመቤታችን በዓልም  ጽጌን በጽጌ ብላ በወርሐ መስከረም  ጀምሮ ለ፵ ቀናት እንዲታሰብ ወስናለች።
ቅዱሱ ቤተ ሰብ ለስደት የተዳረገው በሄሮድስ አጉል ቅንዓት ምክንያት ነው።ምንም እንኳን፦ትንቢተ ነቢያትን፣ጽድቀ ትስብእትን፣ኪዳነ መልከ ጼዴቅን፣ምሳሌ ጽዮንን የፈጸመበት ቢሆንም በሄሮድስ ህሊና ግን፦
ቅንዓት፣ምቀኝነት፣ተንኮል ተንሰራፍተውበት በዲያብሎስ ሀሳብ እየተቃኘ ቅዱሱን ቤተ ሰብ ለማጥፋት ያሳድደው ነበር።
ቅዱሱ ቤተ ሰብ እስከ ምጽአት ድረስ ለሚነሱ ክርስቲያኖች ምሳሌ፣አርአያ፣ምልክት፣መመሪያ ነው።በቅዱሱ ቤተ ሰብ የሆነው ሁሉ በክርስቲያኖች ላይ መሆኑ አይቀርም።ቤተክርስቲያን አሁንም ስደት ላይ ናት።ሄሮድስ አሁንም ማሳደድ ላይ ነው።
ችግሩ የስደተኞች ማረፊያ እንግዳ ተቀባይ የሆነችው ኢትዮጵያም አብራ መሰደዷ ነው።
እንደ ቅዱስ ገብርኤል ስደት ይበቃሻል ተመለሽ የሚላት ምድራዊ ቸር መልአክ እስኪገኝ ድረስ መቸገሯ አይቀሬ ነው።
እኛም የቅዱሱን ቤተ ሰብ ስደት በህሊና እያሰብን የመዓልት ሀሩሩን የሌሊት ቁሩን እናዘክርበታለን።
ከቅዱሱ ቤተሰብ ጋራ በህለሊና የሚሰደዱ አባቶቻንን እናቶቻችን በጽጌ ወራት ያላቸውን ጠላውን ጠምቀው ዳቦውን ይዘው ከመንገድ ወጥው ያለፈ ያገደመውን የወጣ የወረደውን ስለ አዛኝቷ እያሉ ይዘክራሉ ያዘክራሉ።
ይሄ በስደቱ ውስጥ ህልው ሁኖ የማሰብ የሰማዕትነት።፣የመስካሪነት ህሊና ነው።
         "ጻዕ ውስተ ኀሠሣሁ ለዘመጽአ ውስተ ኀሢሦትከ፦
                ሊፈልግህ የወጣውን ልትፈልገው ውጣ"አረ.መን.

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

08 Oct, 15:46


         " አስተውሉ"ማቴ.፲፭፥፲
ነገሩን አስልቶ፣ሀሳቡን በልቶ፣ትናንትን አጥንቶ፣ዛሬን ሠርቶ ለነገው ትውልድ ለማስረከብ ሲባል ራስን ሰጥቶ፣በልቡና ማሰብ፣ማማጥ እና ማስተዋል ያስፈልጋል።
ይልቁንም ነገን በራእይ ህሊና ሁኖ አስተውሎ ትኩርርር ብሎ ማየት ይገባል።
አስተውለው ራስን ሰጥተው ካልሠሩበት ከዛሬው ሌሊት የነገው ሌሊት ይጨልማል።አስተውለው ራስን ሰጥተው ከሠሩ ደግሞ ከዛሬው ሌሊት የነገ ሌሊት ይቀላል።
አስተውሎት በብዙ መንገድ ትገኛለች፦
• 1.በተፈጥሮ የሚገኝ አስተውሎት
• 2.በትምህርት የሚገኝ አስተውሎት
• 3.በልምድ የሚገኝ አስተውሎት
• 4.በሁኔታ ግዴታ የሚገኝ አስተውሎት
• 5.በመገለጥ የሚገኝ አስተውሎት አለ።
ማስተዋል በልምምድ ያድጋል።ሁሉም ነገር ሂደታዊና ልምምዳዊ ነውና።
አስተውሎ ዓላማን መለማመድ ጠቢብና የዋህ ያደርጋል።
ልምምዱ ለመልካም ዓላማ ከሆነ ፖሮግራሙ እንጂ ትምህርቱ አይቋረጥም።
ልምምዱ ለባዶነት ከሆነ ግን ህክምናው ከባድ ነው።
"ልማድ ከሰይጣን ይከፋል"እንዲሉ።ከሰው የተሠወረ ሰው ከጥበብ የተሠወረ ግብ ይሆናል።
ስለ ሁሉም የግድ ማስተዋል አለብን፣እናት አምጣ ልጅ እንደ ምትወልድ ልቡናም አምጦ ማስተዋልን ይወልዳል።በአስደማሚ  አስተውሎት  ከመከራው መውጫ መንገዳችንን በመፈለግ እንለማመድ።
ምን ብናደርግ ነው ቤተ ክርስቲያን ከገጠማት መከራ የምትወጣው?
የመፍትሄ መልሱን ካገኘነው ከማውራት ወደመሥራት እንሸጋገራለን።
ብለን ነበር፣አስበን ነበር፣አቅደን ነበር...መፍትሄ አይደለም።መፍትሄው አስተውሎ ተገቢውን ማድረግ ነው።
እንደ አነጣጣሪ ሰው ሀሳብን ከተግባር ጋራ አስተውሎ ወደነገ ማነጣጠር ነው።
           "አስተውሉ እንጂ ሞኞች አትሁኑ።"ኤፌ.፭፥፲፯ ብሎ ጠቢብ ሐዋርያ እንዳስተማረን።ተላላነት ነገን አታሳይም አሁን ብቻ ናት።
"የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ በዓይናችሁ ፊት  ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው?" ኤፌ.፫፥፩
ገሐዱን ዓለም፣ገሐዱን ሰቆቃ፣ገሐዱን ችግር..አስተውለን ተረድተን ለነገ የሚተርፍ ተግባርን እንዳንተገብር የሚጎትተን ምንድን ነው?
  መፍትሄው ከአስተውሎት ቀጥሎ ቀልጠፍ ብሎ መሥራት ዘግየት ብሎ ማውራት ነው።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

07 Oct, 05:56


      -ሲኖሩ በሰማዕትነት ሲሞቱ በታሪካዊነት፦
በምድር ላይ መኖር የምንችለው ባአጭር ዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ነው።
ከሞት በኋላ ሁለተኛ ለብዙ ዘመናት መኖር የምንችለው ግን በመልካም ታሪካችን ነው።
ታሪክ የሠራ ሰው ዳግም በታሪክ ህልውና ውስጥ ሕያው ሁኖ ሲወሳ መኖር ይችላል።
ህያው አድራጊ ታሪክ ደግሞ ዝም ብሎ በስንፍና አይሠራም።
ራስን ሰጥቶ ሞትን ንቆ አጥቅቶ ነገን አልሞ በመሥራት ነው እንጂ።
ይልቁንም ትንሣኤ ሙታን ያለው ሰው ሁልጋዜም ታሪካዊ ሕያውነትን በህሊናው ማየት ግድ ይለዋል።
ስለሆነም ከሞት በኋላ በታሪክ ህልውና ውስጥ ለመኖር ምን እየሠራን ነው?
ወይስ አሁናዊ ብቻ ሁነን ለመቅረት ነው የምንፈልገው?
ክፉ ሰው ርኩስ መንፈስን አምኖ  ምእመናንን ለማጥፋት ለክፉ ታሪክ ከተነሣ እኛ መንፈስ ቅዱስን አምነን ትናንትን ለትውልድ ለማስረከብ የነገ መልካም ታሪክን ለማንበር መነሣሣት ግድ ይለናል።
ምክንያቱም ዛሬ ባለችን በዓላማ በቁርጠኝነት ራሳችንን ሰጥተን ካልሠራን ለነገ  ትውልድ ታሪክም ሃይማኖትም አይኖረንም።
በታሪክ ህልውና ውስጥ እንዳናይ የሚያደርገን ገርጋሪያችን ፍርሀት እና አስመሳይነት ነው።
ፈሪ ሰው ደግሞ የክርስቶስ መስቀሉን መሸከም አይችልም።
መስቀልን ያልተሸከመ ሰው ደግሞ መከራ አይንካኝ ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ ሲል የሰማዕትነት ክብር ታመልጠዋለች።
ሲኖሩ በሰማዕትነት ሲሞቱ በታሪካዊነት ለመገለጽ ካሰቡ ፍርሀትን እና አድርባይነትን  እንደ ሸረሪት ድር ገፎ መጣል ግድ ይላል።
መስሎ መኖር እና አድርባይነት ለስለላሳ ኑፋቄ ነው።
በምድር ላይ ማን ይፈራል? ሞትን እንዳንፈራው? ትንሣኤ ሙታን አለን።
አግባብስ ያለታሪክ ያለ ሃይማኖት እንዳይቀር የነገውን ትውልድ መፍራት ነው።
ለነገ አለማሰብ የነገውን ትውልድ በግልጽ መበደል ነውና።
ትናንትን እንደሚገባ ከአባቶቻችን እንደተቀበልነ ዛሬም በሰማዕትነት የተቀበልነውን አደራ እየጠበቅነ ለነገው ትውልድ የማስረከብ ሀላፊነት አለብን።
የነገ ታሪክ ሰነፎች ተቀምጠው ሳሉ እንደ ፈጣን ወፍ ማረፊያ አጥቶ በጊዜ ነፋስ ላይ በርሮ መሄዱ አይቀርም።
መሥራት ባይቻል እንኳን ለሚሠሩ ሰዎች እንቅፋት ላለመሆን መጣር ተገቢ ነው።
ከህሊናም ከታሪክም ጋራ መጣላት ትልቅ ድክመት ነው።
መሆን ያለብንን ሳንሆን መሆን ያለበት አይሆንም።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

29 Sep, 11:52


     
        ፍርሀት ትንሣኤ ሙታንን አለማመን ነው።
ትልቁ ኑፋቄ ፍርሀት ነው።ጴጥሮስ በዕለተ ዓርብ በልቡ አምኖ በአፉ ጌታውን አላውቀውም ብሎ የካደው ስለፈራ ነው።ጴጥሮስ የፈራለታ ከሀዲ ነው።ጴጥሮስ የጨከነለታ ሃይማኖተኛ ነው።እየፈሩ አባት መሆን አይቻልም ከሀዲ መሆን ግን ይቻላል።እየጨከኑ ግን  ከክርስቶስ ፍቅር ማን ይለየኛ? በማለት አባት መሆን ይቻላል።የነበረን ያጣነው የሚያስፈልገን የረሳነው ምንድን ነው?
እንደ ይሁዳም በአፍ እያመኑ በተግባር መካድ ሐዋርያ አያደርግም።ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ ብሎ ጌታውን የመሸጥ ተልእኮ ነው እንጂ።እኛን የደረሰብን የቱ ነው?
አሁን አሁን እንደ ክርስቶስ ለምእመናንን ቤዛ ሁኖ ፊት ለፊት እነሆ መንገዱ ብሎ ያለ ፍርሀት በሃይማኖት የሚመራ ሕያው አባት ማግኘት መታደል ነው።
ሕያው አባትነት መስቀላዊ መሪነት ነው።መሪነት ደግሞ  ሥልጣን ሲይሆን የሕይወት ለውጥን የሚሻ አስተሳስብ ነው።
የሕይወት መሪነት ደግሞ ሁነትን የመረዳት እና ስለ በጎቹ ቤዛ የመሆን ግብር ነው
ለበግቹ መቅደም ደግሞ አምላካዊ ምግብን ያለሀኬት የማስቀጠል ጴጥሮስነትን የመትከል ተግባር ነው።
ጴጥሮስነትን መትከልም ሙሴነት ነው እየተጎዱ ማብራት እየተቸገሩ መሥራት ያልተለየው ግብር ይህ ነውና።
ፍጹማዊ መሪነት ክርስቶስ ነው፦እየተሰቀሉ ማሳየት።ሳይሰቀሉ ክርስቶስነት ሳይቀበሩ ትንሣኤ የለም።
ፍርሀት የሸበበው ሰውነት ወንጌላዊ ክርስቶሳዊ አይደለም።በክብር ለመነሣት መከራ መቀበል አይገባምን? "ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባል።"የሐ ሥራ.ምዕ.፭፥፳፱

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

29 Sep, 02:24


ማፍዘዣ ቃላቶች
1.“አታስቡ እግዚአብሔር ያውቃል”
2.“ዘመኑ (ጊዜው) ስለደረሰ ነው!”
3.“ይህ ሊሆን ግድ ነው፡፡”
4.“ሃይማኖት ትመነምናለች እንጂ አትበጠስም”
5 “ክርስቶስ እንዲህ አላስተማረም ዝም ብላችሁ ተሰቀሉ ነው ያለን”
6.“ግራህን መልሰህ ስጠው”
7.ቅዱስ ሲኖዶስ አልወሰነም”
8."የሚመለከታቸው አካላት አልፈቀዱም፡፡"
9.“እኛ ከአባቶች በላይ አናውቅም”
10.“መችስ የተነገረው ትንቢት አይቀር”
11.“የሚሆነው እግዚአብሔር የፈቀደው ነው፡፡” 12.“የሚሆነው ከመሆኑ ላይዘል!”
13.“8ኛው ሺህ ስለሆነ ነው!”
14.“ዘመኑ የሥራ ዘመን አይደለም!”
15.እነ እገሌ ይሠሩታል ችግር የለም፡፡
16. ማኅበሩ ሳለ ቤተ ክርስቲያን አትፈርስም
17. የእኛ ሥራ መጸለይ ብቻ ነው።.....
የመሳሰሉ ቃላትን እየተጠቀሙ ሰውን የሚያደነቁሩ ሰዎች ምን እያሉ ነው?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

28 Sep, 17:14


🌠 መስቀል
መስቀል፦  አይሁድ በክፋታቸው አህዛብ በሥጋዊ ጉልበታቸው ተባብረው በክርስቶስ ይሙት በቃ ተፈርዶበት  ክርስቶስ ተሰቅሎ ዓለምን ካዳነ በኋላ ለክርስቲያኖች ሁሉም የድል ማድረጊያ መሳሪያ ሆኖ ተሰጥቷል ያችም ዕለተ ዓርብ ናት ።

ይህንንም መስቀል አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ገቢረ ተአምራት ወመንክራት እያደረገ ሙት እያስነሳ ድውይ እየፈወሰ አጋንንት እያስወጣ አስራ ሦስተኛ ሐዋርያ ሆኖ  ዓለምን ሁሉም ወደክርስትና ጠራው በዚህም ተበሳጭተው ስልሳ ክንድ ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት በላዩም ቆሻሻ ደፉበት በዚህ ጉድጓድም ፪፻፺፪ (ሁለት መቶ ዘጠና ሁለት ) ዓመት ኖረ
ግን ከመሬት ብቻ ሳይሆን ከክርስቲያኖች ልቡናም ተቀብሮ ነበረ !!!!!

በ፫፻፳፮ (በሦስት መቶ ሃያ ስድስት ) በንግሥት እሌኒ አማካኝነት መስከረም አስራ ሰባት ቁፋሮ ተጀምሮ መጋቢት ፲ (አሥር) ከተቀበረበት ጉድጓድ ወጣ ቤተመቅደስም ሰርታ አስቀመጠችው ።

በ፮፻፲፬ (በስድስት መቶ አስራ አራት) የፋርስ ነገሥታት ቅድስት ለገር ኢየሩሳሌምን ወረው ቤተመቅደሱን አቃጥለው ሕዝቡን ገድለው ንዋየ ቅድሳቱን ዘርፈው ሲሄዱ መስቀሉን ከሁለት ዲያቆናት ጋራ ወደፋርስ አወሰዱት በንጉሥ ሕርቃል አማካኝነት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ ።

በ፯፻፴፰ (በሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት መቶ) ዓም ዓረቦች ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌምን ወረሯት ግን በጊዜው ኢየሩሳሌምን እንዲያስተዳድር የተላከው ንጉሥ ዑመር ከሊፋ ደግ ነበርና ክርስቲያኖችን አላሳደደም አምልኳቸውን አልከለከለም አብያተ ክርስቲያናቸውን አላቃጠለም ነገር ግን አስተዳደሩ የዓረባውያን ነውና መስቀሉ በ፯፻፸፰ (በሰባት መቶ ሰባ ስምንት ) ዓም በሦተኛው ዮሐንስ ሊቀጳጳስ ዘመን ወደእስክንድርያ መጣ።

በአስራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዓፄ ዳዊት ሁለተኛ ዘመነ ንግሥና የግብፁ ንጉሥ በግብፅ ክርስቲያኖች ላይ መከራ አጸናባቸው ሊቀጳጳሱን አቡነ ሚካኤልንም ወደ እስር ቤት ወረወራቸው
በዚህም ምክንያት በሮምያ በቁስጥንጥንያ በሦርያ በአርመን በእስክንድርያ ያሉ ክርስቲያኖች አድነን ብለው ወደንጉሥ ዳዊት ላኩ እርሱም ቀናዒ ለሃይማኖት ነውና
አስር ዕልፍ ፈረሰኛ
አስር ዕልፍ ባለግመል
አስር ዕልፍ ባለበቅሎ ወታደር አስከትሎ ወረደ ልዩ ስሙ እስዋን ከሚባል የኢትዮጵያና የግብፅ ድንበር ድካ ላይ ሲደርስ አባይን አሰገደበ ወደሱዳንም መለሰው የግብጹ ንጉሥም እጅ መንሻ ጨምሮ ምጽንታ አቀረበ እጅ መንሻውን መልሶ የጌታየን መስቀል ስጡኝ ብሎ እጅ መንሻ ጨምሮ ላከ ይገባዋል ብለው ሉቃስ የሳላቸውን ሰባት ስዕላተ ማርያም ዮሐንስ የሳለው ኵርዐተ ርዕስ ስዕለ ክርስቶስ ሰፍነጉን ሰንሰለቱን አክሊለ ሦኩን ...አድርገው ላኩለት መስከረም አስር እስዋን ከምትባል ቦታ ላይ ተቀበለ በዚህም ምክንያት መስከረም አስር ዓፄ መስቀል የሚባል ስያሜ ተሰጥቶታል
መስከረም አስራ ሰባት በዓል አድርጎ ወደኢት ዮጵያ ሲመለስ ስናር ከሚባል ቦታ በድንገት ጥቅምት ዘጠኝ አረፈ ።

ከዚያ በኋላ ልጁ ዘርዐያዕቆብ ስመ መንግሥቱን ቆስጠንጢኖስ አሰኝቶ ነገሠ ቆስጠንጢኖስ የተባለበት ምክንያትም ያኛው ቆስጠንጢኖስ በዝንቱ ትዕምርተ መስቀል ትመውዖሙ ለፀርከ
በዚህ የመስቀል ምልክት ጠላቶችህን ድል ትነሳቸዋለህ የሚል ራዕይ አይቷል ዘርዐ ያቆብም አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል
መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ አስቀምጥ የሚል ራዕይ አይቷልና ነው ።
ከዚህ በኋላ መስቀልኛ ቦታ እየፈለገ ሦስት ዓመት ከዞረ በኋላ በግሸን ደብረ ከርቤ በ፲፻፬፻፵፮(በአንድ ሺኽ አራት መቶ አርባ ሁለት) ዓም መስከረም ሃያ አንድ ቀን የእመቤታችን በዓል በሚከበርበት እለት አስቀምጦታል ።
ከዚያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደማቅ እያከበረችው ትገኛለች ።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

28 Sep, 17:14


🌠 መስቀል
መስቀል፦  አይሁድ በክፋታቸው አህዛብ በሥጋዊ ጉልበታቸው ተባብረው በክርስቶስ ይሙት በቃ ተፈርዶበት  ክርስቶስ ተሰቅሎ ዓለምን ካዳነ በኋላ ለክርስቲያኖች ሁሉም የድል ማድረጊያ መሳሪያ ሆኖ ተሰጥቷል ያችም ዕለተ ዓርብ ናት ።

ይህንንም መስቀል አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ገቢረ ተአምራት ወመንክራት እያደረገ ሙት እያስነሳ ድውይ እየፈወሰ አጋንንት እያስወጣ አስራ ሦስተኛ ሐዋርያ ሆኖ  ዓለምን ሁሉም ወደክርስትና ጠራው በዚህም ተበሳጭተው ስልሳ ክንድ ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት በላዩም ቆሻሻ ደፉበት በዚህ ጉድጓድም ፪፻፺፪ (ሁለት መቶ ዘጠና ሁለት ) ዓመት ኖረ
ግን ከመሬት ብቻ ሳይሆን ከክርስቲያኖች ልቡናም ተቀብሮ ነበረ !!!!!

በ፫፻፳፮ (በሦስት መቶ ሃያ ስድስት ) በንግሥት እሌኒ አማካኝነት መስከረም አስራ ሰባት ቁፋሮ ተጀምሮ መጋቢት ፲ (አሥር) ከተቀበረበት ጉድጓድ ወጣ ቤተመቅደስም ሰርታ አስቀመጠችው ።

በ፮፻፲፬ (በስድስት መቶ አስራ አራት) የፋርስ ነገሥታት ቅድስት ለገር ኢየሩሳሌምን ወረው ቤተመቅደሱን አቃጥለው ሕዝቡን ገድለው ንዋየ ቅድሳቱን ዘርፈው ሲሄዱ መስቀሉን ከሁለት ዲያቆናት ጋራ ወደፋርስ አወሰዱት በንጉሥ ሕርቃል አማካኝነት ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ ።

በ፯፻፴፰ (በሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት መቶ) ዓም ዓረቦች ቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌምን ወረሯት ግን በጊዜው ኢየሩሳሌምን እንዲያስተዳድር የተላከው ንጉሥ ዑመር ከሊፋ ደግ ነበርና ክርስቲያኖችን አላሳደደም አምልኳቸውን አልከለከለም አብያተ ክርስቲያናቸውን አላቃጠለም ነገር ግን አስተዳደሩ የዓረባውያን ነውና መስቀሉ በ፯፻፸፰ (በሰባት መቶ ሰባ ስምንት ) ዓም በሦተኛው ዮሐንስ ሊቀጳጳስ ዘመን ወደእስክንድርያ መጣ።

በአስራ አራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዓፄ ዳዊት ሁለተኛ ዘመነ ንግሥና የግብፁ ንጉሥ በግብፅ ክርስቲያኖች ላይ መከራ አጸናባቸው ሊቀጳጳሱን አቡነ ሚካኤልንም ወደ እስር ቤት ወረወራቸው
በዚህም ምክንያት በሮምያ በቁስጥንጥንያ በሦርያ በአርመን በእስክንድርያ ያሉ ክርስቲያኖች አድነን ብለው ወደንጉሥ ዳዊት ላኩ እርሱም ቀናዒ ለሃይማኖት ነውና
አስር ዕልፍ ፈረሰኛ
አስር ዕልፍ ባለግመል
አስር ዕልፍ ባለበቅሎ ወታደር አስከትሎ ወረደ ልዩ ስሙ እስዋን ከሚባል የኢትዮጵያና የግብፅ ድንበር ድካ ላይ ሲደርስ አባይን አሰገደበ ወደሱዳንም መለሰው የግብጹ ንጉሥም እጅ መንሻ ጨምሮ ምጽንታ አቀረበ እጅ መንሻውን መልሶ የጌታየን መስቀል ስጡኝ ብሎ እጅ መንሻ ጨምሮ ላከ ይገባዋል ብለው ሉቃስ የሳላቸውን ሰባት ስዕላተ ማርያም ዮሐንስ የሳለው ኵርዐተ ርዕስ ስዕለ ክርስቶስ ሰፍነጉን ሰንሰለቱን አክሊለ ሦኩን ...አድርገው ላኩለት መስከረም አስር እስዋን ከምትባል ቦታ ላይ ተቀበለ በዚህም ምክንያት መስከረም አስር ዓፄ መስቀል የሚባል ስያሜ ተሰጥቶታል
መስከረም አስራ ሰባት በዓል አድርጎ ወደኢት ዮጵያ ሲመለስ ስናር ከሚባል ቦታ በድንገት ጥቅምት ዘጠኝ አረፈ ።

ከዚያ በኋላ ልጁ ዘርዐያዕቆብ ስመ መንግሥቱን ቆስጠንጢኖስ አሰኝቶ ነገሠ ቆስጠንጢኖስ የተባለበት ምክንያትም ያኛው ቆስጠንጢኖስ በዝንቱ ትዕምርተ መስቀል ትመውዖሙ ለፀርከ
በዚህ የመስቀል ምልክት ጠላቶችህን ድል ትነሳቸዋለህ የሚል ራዕይ አይቷል ዘርዐ ያቆብም አንብር መስቀልየ በዲበ መስቀል
መስቀሌን በመስቀልኛ ቦታ አስቀምጥ የሚል ራዕይ አይቷልና ነው ።
ከዚህ በኋላ መስቀልኛ ቦታ እየፈለገ ሦስት ዓመት ከዞረ በኋላ በግሸን ደብረ ከርቤ በ፲፻፬፻፵፮(በአንድ ሺኽ አራት መቶ አርባ ሁለት) ዓም መስከረም ሃያ አንድ ቀን የእመቤታችን በዓል በሚከበርበት እለት አስቀምጦታል ።
ከዚያ ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በደማቅ እያከበረችው ትገኛለች ።

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

26 Sep, 06:08


ደመራው የመስቀል መቆፈሪያ እንጂ የመስቀል መቅበሪያ አይደለም።
እየሆነ ያለው የቱ ነው? ቀበራው ነው?ወይስ ደመራው? በዓመት በዓመት መቅበር እንጂ ማውጣት ከሌለው የደመራው ጥቅም ዘልማድ መሆኑ ነው።
የተቀበረውን ላያወጡ እየደመሩ ማቃጠል ማስመሰል ብቻ ነው።
በደመራው አቃጣዮች አሉ። የተቀበረውን የሚያወጡ ያለውን የማያስቀብሩ ሰዎች ግን የዓመቱ ደመራ ያልገባቸው ይባላሉ።
የዓመት መስቀልን የዓመት ደመራን እያከበርን  ሁልጊዜ ያለ የሕይወት መስቀልን የሕይወት ደመራን ከረሳን ቱሪስቶች እንጂ ክርስቲያኖች አይደለንም።
የደመራው ዓላማኮ ያለውን ለመጠበቅ የጠፋውን ለመመለስ የተቀበረውን ለማውጣት ነበር።ደመራችን በተቃርኖ ሲደመር ያለንን ይቀብራል ያጣነውን ያስረሳል።
እሌኒ በደመራዋ መስቀሉን ከተቀበረበት ቆፍራ አውጥታዋለች።
እኛም ወይ የተቀበረውን ቆፍረን እናውጣ ካልሆነ ደግሞ መስቀሉን ለመቅበር አንደምር።
የዘመናችን የመስቀል ጠላቶች ሁልጊዜም ቀበራ ላይ ናቸው።
የመስቀል ወዳጆችስ?

ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት

23 Sep, 15:05


             ፦ነገ ይታያል ወይ?
ያለ ትምህርት ነገ ምንድን ነው?
ነገ የማን ነው?
ዘንድሮም እንደ አምናው በብዙ ቦታዎች ፕሮፓጋንዳ እንጂ ትምህርት የለም።የሕጻናት እድሜ ደግሞ ያለ ትምህርት እየቀጠለ ነው።በዚህ መካከል ነገን ስናስበው ምን አሳሳቢ ነው።
በእጃቸው ያለውን ትምህርት ቤት አስበው ከዘጉብን በእጃችን ያለውን አብነት መጠቀም አይሻልም ወይ? ነገን ማየት የሚቻለው በዛሬ ተግባር ነው።
ትናንት የዛሬ ውጤት ነው።ዛሬ ደግሞ የነገ ምርት ነው።ስለ ነገ መጨነቅም ትክክለኛ ዕይታ ነው።
ስለሆነም የነገ ተረካቢዎች ሁሉም ሕጻናት ወደ አብነት ይሂዱና ነገን እንሣልባቸው።ልጅን አብነት አለማስተማር ግን  ወንጀል መሆን አለበት።
በሁሉም አካባቢዎች አብነት መማር ዕሴት ባህል  እስኪሆን  እንሥራ።የሰላም ዘመን  እስኪመጣ እጃችን ላይ ባለን ትምህርት ዘመኑን እንዋጅበት።
የአብነት ትምህርቱን እንዴት ሁላዊ አድርገን እናስጀምር?
1ኛ.በቅድሚያ  እንደ ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ሁኖ የሚሠራ ከሕዝቡ መካከል የታመነባቸውን ሰዎች  መመደብ።
2ኛ በየ ገጠሩ በየደብሩ በየቀበሌው በየእድሩ በየሰንበቴው ስለ አስፈላጊነቱ ግንዛቤ መፍጠር መነጋገሪያ ማድረግ።
3ኛ ሕዝቡ የመረጣቸው ተሰሚ ሰዎች ሀላፊ ሁነው እንዲያስፈጽሙ  ሕዝባዊ ትዕዛዝ ማውረድ።
4ኛ አብነቱን ለሊያስተምሩ የሚችሉ ካህናትን መምህራንን ሰብስቦ ግንዛቤ መስጠት እና ማወያየት።
5ኛ. ሁሉም ደብሮች አስገዳጅ  አባታዊ ትምህርታዊ ትዕዛዞችን ለህብረተ ሰቡእ እንዲያስተላልፉ ማድረግ።ልጁን የማያስተምር ውጉዝ መባል አለበት።
6ኛ ለተፈጻሚነቱ  በሕዝቡ የተወከሉ አካላት ክትትል እና ምዘና ማድረግ አለባቸው።ማንበብ መጻፍ የማይችል ልጅ ሊኖረን አይገባምና።
7ኛ መንፈሳውያን ማኅበራትን እድሮችን ሰበካዎችን..የድርሻ ሀላፊነትን ወስደው እንዲሠሩ  ማነሳሳት።
8ኛ.አስተማሪ  የሆኑ ትምህርት ቤቶችን ለሌላው ማሳያ እንዲሆኑ የሚድያ ሽፋን መስጠት።
9ኛ ከአብነት ጎን ለጎን  አራቱን የሒሳብ ስሌቶችን የሚሰጥ ሰው ማዘጋጀት።
አለማስተማር ወንጀል መሆን አለበት።ልጁን ያልስተማረ የነገ ሀገር የለውም።የአብነት ትምህርት የትውልዱ አቢዮት መሆን አለበት።

6,818

subscribers

76

photos

7

videos