ከመጽሐፍት መንደር💠 @manbabemulusewyaderegal Channel on Telegram

ከመጽሐፍት መንደር💠

@manbabemulusewyaderegal


አንብብ አዕምሮህ ልክ አንደባህር ይሰፋል። ወንዞችም ለአንተ መገበር ይጀምራሉ። አንተ ወደ ሰዎች ሳይሆን ሰዎችም ወደአንተ ይመጣሉ። ማንብብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!! አንብብ ብታነብ የሚቀርብህ ድንቁርና
🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩
🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨
🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥

ለማንኛውም አስተያየት
@manbabemuluyadergal_bot

ከመጽሐፍት መንደር💠 (Amharic)

ከመጽሐፍት መንደር💠 አንብብ አዕምሮህ ልክ አንደባህር ይሰፋል። ወንዞችም ለአንተ መገበር ይጀምራሉ። አንተ ወደ ሰዎች ሳይሆን ሰዎችም ወደአንተ ይመጣሉ። ማንብብ ሙሉ ሰው ያደርጋል!! አንብብ ብታነብ የሚቀርብህ ድንቁርና🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟩🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟨🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥🟥ለማንኛውም አስተያየት @manbabemuluyadergal_bot

ከመጽሐፍት መንደር💠

06 Feb, 17:45


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያ ሶስት

በማግስቱ የናፈቀው ቢሮ የገባው አራት ሰዓት አካባቢ ነበር….የማታው ስካር አንጎበሩ ሙሉ በሙሉ አለቀቀውም…አሁንም ጭንቅላቱን እየወቀረው ነው፡፡ለፀሀፊው መምጣቱን
ስላልነገራት አልገባችም…ከፍቶ ገባና ቁጭ አለ ..የሚሰራው ስራ ስላልነበረ የሚያደርገው ነገር ግራ ገባው..ስልክ አውጥቶ ደወለ፡፡
‹‹እንዴት ነሽ…ለሊሴ?››
‹‹ደህና ነኝ ሰለሞን…እንዴት ነው ስራ?››
‹‹አሪፍ ነው..አሁን ተመልሼለሁ…ቢሮ ነው ያለሁት››
‹‹ውይ ለምን ሳትነግረኝ..ቀድሜ ገብቼ አፀዳድቼ ጠብቅህ ነበረ እኮ››
‹‹አይ ችግር የለውም..ቢሮው አሁንም ንፅና የተስተካከለ ነው››
‹‹አዎ እሱማ በሶስት ቀን አንዴ ከፍቼ አናፍሰዋለው….እና ስራህን ጨረስክ ማለት ነው?››
‹‹አይ አልጨረስኩም…በመሀል የሶስት ቀን እረፍት ስላለኝ ነው የመጣሁት…ለመሆኑ ያንቺ ነገር እንዴት ሆነ?››
‹‹የቱ?››
‹‹የሁለቱ ፍቅረኞችሽ ነገር?››
ለሊሴ ሰለሞን ባቀረበላት ሀሳብ መሰረት ከሁለት ፍቅረኞቾ መካከል አንዱን ለባልነት ለመምረጥ ምታደርገውን ጥረት ወዲያው ነበር የጀመረችው ….መጀመሪያ ነጋዴውን ለአንድ ወር ላታገኘው እንደማትችል ነግራ ከመንግስት ሰራተኛው ጋር ነበር የቀጠለችው..ሲደውልላት ትሄዳለች..ዝም ሲላት ትደውልለታልች….ከስራ መልስ ሳታገኘው ወደቤት አትገባም…እሁድ ቢያንስ ግማሹን ሰዓት ከእሱ ጋር ነች፡፡ይበልጥ ትኩረቷን ሰብስባ ከእሱ ጋር ባሳለፈች መጠን በፊት ከምታውቀው በላይ እያወቀችው …በፊት ከምታዳምጠው በላይ እያዳመጠችው መጣች፡፡አሁን ያለበትን የኑሮ ደረጃ ብቻ ሳይሆን ..

የወደፊት እቅዶቹንና እነዛን እቅዶች ለማሳካት እያደረገ ያለውን ተጋድሎም እየተረዳችና እየተገነዘበች መጣች…..እሱ ላይ ያላት ቅሬታ ባገባው እኔን አኑሮ ቤተሰቦቼንም እንድረዳ የሚያበቃኝ ህይወት ሊሰጠኝ አይችልም የሚል ነበር…አሁን ስታስበው ግን ያንን ከእሱ ብቻ መጠበቅ እንደሌለባት ነው የገባት…እሱ ባለው ቁርጠኝነት ላይ እሷ ተጨምራበት ካገዘችውና ከጎኑ ሆና አብራው ከታገለች ጎዶሎው ሊሞላ የሚችል አይነት እንደሆነ ተረድታለች…ግን ውሳኔ ላይ ከመድረሷ በፊት ለእሱ የመደበችለት ወር ተገባደደ እና ለዛኛው የሰጠችውን ተመሳሳይ ምክንያት ሰጥታ ..ለአንድ ወር ያህል ልትደውልለትም ሆነ ልታገኘው እንደማትችል ነገራ ወደነጋዴው ሄደች፡፡
በእውነት ነገዴው ጋር ልክ እንደወትሮ ሁሉ ነገር ተሰርቶ ያለቀ ሆኖ ነው የጠበቃት…ቤቱ የተዘጋጀ..እቃዎቹ የተደራጁ ናቸው…አዎ እያንዳንዱን ሀብቱንና አኗኗሩን ተራ በተራ አሳያት፣ቀጥታ እንዳገባችው ሕይወቷን ወደመስራት ሳይሆን የተሰራ ህይወት ውስጥ ገብቶ ለመኖር መሞከር ብቻ እንደሚጠበቅባት ተረዳች ፣ግን ለምን ልቧ ወደኃላ እንደሚጎትታት ግልፅ ሊሆንላት አልቻለም‹‹…ታግዬ ያላሸነፉኩት በሌላ እጅ የተሰራ ህይወት ምን ትርጉም ይኖረዋል?››እራሷን ጠየቀች… መልሱ ቀላል አልነበረም….፡፡
ሁሉንም ሂደት አንድ በአንድ ዘርዝራ አስረዳችው፡፡ ሰለሞንም‹‹እና ምን ተሰማሽ?››ሲል ጠየቃት
‹‹አሁንም እንደተወዛገብኩ ነው…ግን በአእምሮዬ ውስጥ የሚመላለሱ ጥያቄዎች በፊት ከሚመላለሱት የተለዩ ናቸው…እንግዲህ እኔ በህይወቴ ጠንከር ያሉ ውሳኔዎችን የማስተላለፍ ከፍተኛ ድክመት እንደለብኝ ነው የተረዳሁት፡፡››
‹‹አይ እንደዛ አይመስለኝም …አንቺ ቀሪ ህይወትሽን አብሮሽ በደስታ የሚዘልቅና ከቤተሰቦችሽም ጋ ተሰስማምቶ የሚያኮራሽ ለፍፅምነት የተጠጋ ባል እየፈለግሽ ነው….በዚህ ምድር ላይ ደግሞ ለፍጽምና የተጠጋ ነገር መምረጥ ቀላል ነገር አይደለም፡፡አንድ ታሪክ ልንገርሽ..
‹‹ደስ ይለኛል››
ደቀ መዝሙሩ  መምህሩን ‹‹ፍፁምና በህይወታችን እንዴት አድርገን ነው ፍፅማዊ የሆነ ነገር መጎናፀፍ የምንችለው? ሲል ጠየቀው ፡፡ መምህሩም አሰብ አደረገና ‹‹የዚህን መልስ

እንድነግርህ ከፈለክ በፊት ለፊት በር ወደ ግቢው የአትክልት ስፍራ ቀጥ ብለህ ግባ ።በመንገድህ ከምታገኛቸው አበቦች መካከል በጣም የሚያምረውንና ደስ ያሰኘህን ቀንጥስና በጎሮ በር ውጣ …አንዴ ያለፍከውን አበባ ከእንደገና ወደኃላ ተመልሰህ መቅጠፍ አትችልም አሉት።›› አለው ።እሱም ትዕዛዙን አክብሮ እንዳተባለው ወደ አትክልቱ ስፍራ ገባና እስከመጨረሻው ጥግ ከተጓዘ በኃላ ባዶ እጅን በጓሮ በር ወጣ።
መምህሩ ‹‹ለምንድነው አንድ ቀንበጥ አበባ እንኳን ይዘህ መውጣት ያልቻልከው?››ሲሉ ጠየቁት፡፡
‹‹ምርጥ የተባለውን አበባ ወዲያው እንደገባሁ ነበረ ያገኘሁት... ግን የተሻለ አገኛለሁ ብዬ በማሰብ ሳልቀነጥስ ወደፊት ቀጠልኩ .. መጨረሻው ላይም ደረስኩ.. ወደኃላ የመመለስ እድል ስለሌለኝ ባዶዬን ለመውጣት ተገደድኩ›› ሲል መለሰ።
መምህሩ መልሱን ሲሰሙ ፈገግ አሉና ‹‹አዎ! ትክክል ነህ ፤ህይወት እንደዛ ነው ።ፍፁምናን ለማግኘት ይበልጥ በዳከርን ቁጥር ብኩን እየሆንክ ትሄዳለህ።እውነተኛ ፍፁምናን መቼም የትም አታገኝም።››ሲሉ መለሱለት። ‹‹ገባሽ አይደል?››
‹‹አዎ ገብቶኛል››
‹‹እንግዲያው ፍፅም በምናብ አለም ካስቀመጥሽው ወንድ ጋር የሚስማማ ባል እንደማታገኚ አውቀሽ ለሚማጡት 10 ቀናት ሁለቱንም ሳታገኚ አስቢበት..ከዛ ማንኛቸው ናቸው የበለጠ የሚናፍቁሽ..የትኛው ቢያቅፍሽ ትፈልጊያለሽ ….?ማንኛቸው የልጆችሽ አባት ቢሆኑ ይሻላል..?በህልምሽ እየደጋገመ የሚመጣው የትኛው ነው?፡፡ለ10 ቀን አስቢበት፡፡››
‹‹እሺ እንደዛ አደርገላው..ግን አሁን አሁን እየገባኝ ያለው እኔ ከባሌ ምን እጠብቃለው ብቻ ሳይሆን ለባሌስ ምን ይዤለት ሄዳለው…?የሚለውን በጥልቀት ማሰብና መዘጋጀት እንዳለብኝ ነው፡፡ ››
‹‹ጎበዝ ነሽ…ይሄ ትልቅ መረዳት ነው..በይ ደህና እደሪ››
‹‹ውይ …ከመዝጋትህ በፊት…ድፍረት አይሁንብኝና ዛሬ ቤት ለምን አትመጣም››
‹‹ለምን?››
‹‹እማዬ የማሪያም ድግስ አለባት….ማህበርተኞቹ እስከ10 ሰዓት ነው የሚቆዩት 11 ሰዓት ብትመጣ በጣም ደስ ይለኝ ነበር…››
‹‹አረ ተይ››
‹‹ምን አለበት…ቤተሰቦቼ በጣም ነው ደስ የሚላቸው››
‹‹11 ሰዓት ነው ያልሽኝ?፡፡››
‹‹አዎ 11 ሰዓት››
ብቻውን ሆኖ ስለአስቴር እያሰበ ከሚሰቃይ ከሰው ጋር ተቀላቅሎ የባጥ የቆጡን እያወራ ሊረሳት ቢሞክር እንደሚሻለው አሰበእና ‹‹በቃ እሺ መጣለሁ››አላት፡፡
‹‹በቃ አቃቂ ፖሊስ ጣቢያው ጋር ስትደርስ ደውልልኝ..ወጥቼ እቀበልሀለው››
‹‹እሺ ደውላለው››
ስልኩን ዘጋው፡፡ እሺ ማለቱን ፍጽም አላመነም….ጠበል ለመቅመስ ከሜክሲኮ
አቃቂ….ለመሆኑ በህይወቱ ጠበል የተጠራውና ጥሪውን አክብሮ የሄደው መቼ ነው..?ፍጽም አያስታውስም….
እንዳለችው …..እንደደወለላት ደቂቃ ሳታባክን ነው ወጥታ የተቀበለችው….መኪናውን
እዛው አስፓልት ዳር ፓርክ አደረገና ተከትሏት ይዛው ሄደችው.. ግን ወደሚያስደነግጥ ቦታ ነው ይዛው የሄደችው…ይሄንን ግቢ ትናንትና በዚህን ሰዓት መኪና ውስጥ ሆኖ ከአሰሪዎቹ ጋር በመሆን ሲሰልለው ነበር …‹‹ምን አይነት መገጣጠም ነው?››ለለሊሴ ምንም አይነት የመደነቅና የመገረም ስሜት ሳያሳያት ተከተላት፡፡አሁን ነገሮችን ገጣጥሞ ሲያስብ በፀሎት እሱን እንዴት እንዳገኘችውና ስልኩን ከማን እንደወሰደች ተገለፀለት፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

04 Feb, 17:51


‹‹‹አይ ይሄ ለነገሮች ያለን ትርጉም ልዩነት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡እኔ ወላጅ አልባ ብቻ ሳልሆን ዘመድ አልባ በሆንኩበት በዛ ጨለማ ጊዜ እናትና አባትህ ያለምንም ማቅማማት ወደቤታቸው ወስደው ከዛሬ ጀመሮ አንቺም ሌለኛዋ ልጃችን ነሽ አሉኝ፡፡እውነትም እንዳሉት ለእህትህ ስህን የሚደረገው ሁሉ ለእኔም ይደረግልኝ ነበር..ለእሷ ቀሚስ ሲገዛ ለእኔም ዘለውኝ አያውቁም.. ከፓንት አቅም ለእሷ የተገዛው አይነት ለእኔም ይገዛልኝ ነበር… የእውነት ልጃቸው ነበርኩ..ዩኒቨርሲቲ ገብቼ አንድም ወር የኪስ ገንዘብ ለእኔ ከመላክ እረስተውና ዘለውኝ አያውቁም…እና ሁለቱም ሲሞቱ ከእናንተ እኩል ነው ያጣዋቸው…..አንተ የምትወዳቸውን ያህል እኔም ወዳቸዋለው…አሁን የሚናፍቁህን ያህል

እኔንም ይናፍቁኛል..እና እኔ የእውነትም አንተም ወንድሜ እነሱም ወላጆቼ እንደሆኑ ነው የማምነው..ይሄንን እምነቴን ማንም በየትኛውም ሎጂክ ተከራክሮ ሊያስቀይረኝ አይችልም…እምነት ያው ከቃሉም እንደምትረዳው ዝምብለህ ነገሩን በቀና ልብ መቀበል አይደል..እኔም እንደዛው ተቀብዬዋለው…፡፡አሁን እንተ የደም ትስስር የለንም ምናምን ብትለኝ.በአንዱ ጆሮዬ ገብቶ በአንድ ይፈሳል እንጂ በእኔ ስሜት ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም…አንተ እንደፈለከው ማመን ትችላለህ…እህቴ አይደለሽም ልትለኝም ትችላለህ…በግድ ላሳምንህ አልችልም..፡፡››
‹‹ይገርማል… ልጅ እያለንም ጭምር እንዲህ ነገሮችን ውስብስብ ማድረግ ትወጂ ነበር…እሺ አሁን ለምን ተመልሼ እንደመጣሁ ታውቂያለሽ?››
‹‹ያው የሰው ሀገር አይደል ..ደብሮህ ነዋ››
‹‹አይ አይደለም….ከመስፍን ጋር እንደተፋታችሁ ስሰማና ፣አገር ለቆ እንደሄደ ሳረጋግጥ…ዳግመኛ እድሌን ለመመከር ነው..ምን አልባት አሁን እነአባዬና እማዬ በህይወት ስለሌሉ እሺ ብለሽ ፍቅሬን ትቀበይዋለሽ..እኔንም ከቁም ሞት ቀስቅሰሽ ታድኚኛለሽ..ባል አድርገሽ ታገቢኛለሽ ብዬ ነው››
ዝም ብላ በፍዘት ታየው ጀመር…ቡዝዝ ባሉት አይኖቾ እንባ ሞላባቸው…
‹‹ወንድሜ እኔ በጣም ነው የምወድህ..ያንተ ከጎኔ መሆን የሚፈጥርልኝ ጥንካሬና የመንፈስ ከፍታ ልትገምተው አትችልም…አንተ የራስህን ሰው አግኝተህ አፍቅረህና አግብተህ እዚሁ
አጠገቤ አዲስአበባ እንድትኖር ነው የምፈልገው…እባክህ ወንድሜ መልሰህ ጥለሀኝ አትሂድ
..ዳግመኛ እሰደዳለሁ ካልከኝ..በጣም ነው የማዝነው..እራሴንም መቼም ይቅር አልለውም››
‹‹የምታወራው ምንም ሊገባው አልቻለም..እሱ የሚያወራው እሷን ስለማግባት እና አብሮ አንድ ቤት ስለመኖር…እሷ የምታወራው ስለእሱ ዳግመኛ መሰደድ…‹‹ድንገት ሳላውቅ ተመልሼ ሄዳለው ብያት ይሆን እንዴ ?››ሲል እራሱን ተጠራጠረ፡፡
‹‹ኪያ ምን ነካሽ…?ተመልሼ ሔዳለው ብዬሻለው…እንዴ..?››
‹‹አላልከኝም…ግን ወንድሜ በወላጆቻችን አጥንት ይዤሀለው፣ምንም ቢፈጠር ምንም ጥለኸኝ እንደማትሄድ ቃል ግባልኝ››

‹‹እሺ..እንዳልሽ ቃል ገባልሻለው…ምንም ቢፈጠር ምንም ተመልሼ በድጋሚ አልሰደድም፡፡››
‹‹ጥሩ….ማታ የምቀበለው እንግዳ መስፍን ነው››
የቤተሰቦቹን ሞት የሰማ ቀን እንኳን እንዲህ አልደነገጠም‹‹ምን ..?መስፍን….?ከየት…ወጭ አይደል እንዴ?››
‹‹አዎ..ለአለፉት ሁለት ሶስት ወራት ስንደዋወል ነበር..ችግሮቻችን ተነጋገርን ለመፍታት እና የተበላሸውን ግንኙነታንን ለማስተካከል ወስነን አሁን እየመጣ ነው…ዛሬ ሁለት ሰዓት ነው የሚገባው..ቀጥታ ከቦሌ እኔ ነኝ የምቀበለው..እየመጣ መሆኑን ቤተሰቦቹም አያውቁ..ማለቴ ከቦሌ ቀጥታ ወደቤት ነው ይዤው የምመጣው..ልጅንም በጣም ናፍቆል..እና ተነጋግረን ችግሮቻችንን መቅረፍ ከቻልን ነገሮች ወደድሮ ቦታቸው ይመለሳሉ ማለት ነው..ያው ታውቃለህ የፍቺው ጉዳይ ገና ፕሮሰስ ላይ ነው…ያ ማለት አሁንም በህግ ፊት ባልና ሚስቶች ነን››
ድንዝዝ ባለ ስሜት ንግግሯን እስክትጨርስ ዝም ብሎ አዳመጣት…በፍጽም ፀጥታ ነው የተቀመጠው…ሰውነቱ አይንቀሳቀስም…የአይኖቹ ቅንድቦች እንኳን መንቀሳቀስ አቁመው ነበር፣ትንፋሹ መተንፈስም እንዳቆመ አይነት የመታፈን ስሜት እየተሰማው ነው…ንግግሯን ካጠናቀቀች በኃላም እሱ በዝምታው እንደቀጠለ ነው፡፡
ግራ ገባት…የሆነ ነገር እንዲል እየጠበቀችው ነው…እንዲወቅሳት..እንዲረግማት….በእሷ እንዲያማርር እየጠበቀች ነው..እሱ ግን እንደዛ እያደረገ አይደለም…አስፈሪ ዝምታ ላይ ነው፡፡
‹‹ወንድ….ሜ››
‹‹ሂሳብ ክፈይና እንሂድ››ብሎ መኪናውን ቁልፍ ከጠረጴዛ ላይ አነሳና ቀመ ..ወደመኪናው መራመድ ጀመረ…ከቦርሳዋ ብር አውጥታ ጠረጴዛ ላይ ወረወረችና ፈጠን ብላ ከኃላው ተከተለችው፡፡በህይወቱ እደዛሬው ባዶነትና ተስፋ ቢስነት ተሰምቶት አያውቅም..ፍፅም ተስፋ መቁረጥ ማለት ምን ማለት እንደሆነ የገባውም ዛሬ ነው..በቃ መቼም ይህቺን ሴት ማግባት እንደማይችል አምኖ ተቀበለ…ባያገባትም ግን መቼም ደግሞ ማፍቀሩን እንደማያቆም ያውቃል፡፡

እቤት አድርሷት ብዙም ሳይቆይ ነው ወደቤቱ ያመራው፡፡የሚኖረው ወላጀቹ ቤት ነው ሁሉም ወንድሞቹ የራሳቸውን ህይወት መስርተውና የገዛ ቤታቸውን ሰርተው ቤቱን የለቀቁት ገና ወላጆቹ በህይወት እያሉ ነው፡፡እህቱም ሀገር ውስጥ አትኖርም አሁን በብቸኝነት እየኖረበት ያለው እሱ ነው፡፡ወደቤት ሲገባ ሙሉ ጠርሙስ ጎርደን ጅን ይዞ ነበር የገባው….ገና በቀኑ ነው መኝታ ቤቱን ዘግቶ መጠጣት የጀመረው…
ማታ አንድ ሰዓት ሲሆን ጥንብዝ ብሎ ሰክሮ ነበር‹‹ይሄን ያንን ጉረኛ ልትቀበለው ቦሌ አየር ማረፊያ ቆማ ብርድ እያንቀጠቀጣት ነው››አለ..አሳዘነችው…‹‹ለእሷ የምገባት እኔ ነበርኩ….››ማልቀስ አማረው..እዬዬ ብሎ ማልቀስ አማርው..ግን ማድረግ አልቻለም፡፡ስልኩን ከኪሱ አወጣና ‹‹ማውራት ከቻልሽ ደውይልኝ ››ብሎ ፃፈና ለከ..
ከ5 ደቂቃ በኃላ ተደወለለት‹‹ወይ እግዜር ይስጥሽ…አትደውይልኝም ብዬ ፈርቼ ነበር››
‹‹ምነው? ችግር አለ እንዴ…?ወላጆቼ ምን ሆኑ?››
‹‹‹እነሱ ሰላም ናቸው..በጣም ሰላም ናቸው…ዛሬ አዲስ አበባ ተመልሰናል..እነሱም እቤታቸው ናቸው….እኔ ግን…››ሲያወራ አፉ ይኮለታተፋል..
‹‹ምነው ?አንተ ምን ሆንክ?››
‹‹ተሰብሬለሁ…ሌላ ማወራው ሰው ስለሌለን ነው አንቺ ጋር የደወልኩት…አይገርምም ደህና ጓደኛ እንኳን የለኝም….ቢኖረኝም እንዲህ አይነት ነገር የምነግራቸው አይደሉም››
‹‹ወይኔ በፈጣሪ..እስኪ የሆንከውን ንገረኝ…?.››
‹‹በፀሎት…››
‹‹ወዬ››
‹‹አሁን ካለሽበት መጥተሸ አጠገቤ ብትሆኚና ብታጣጪኝ ደስ ይለኝ ነበር››
‹‹እኔም ደስ ይለኝ ነበር…እይዞህ አንተ ብዙ ነገር የምታውቅ ሰው አይደለህ..?››
‹‹ማወቅ ምን ይሰራል…በፍቅር ስትንኮታኮቺ እኮ ያንቺ ማወቅ እርባነ ቢስ ነው፡፡እኔ እንደውም ይሄንን የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ የሚባለውን ጫወታ መተው አለብኝ..አዎ ፍቃዴን መልሼ ቢሮዬን ዘጋለሁ…››

‹‹ለምን ..ያ ደግሞ ምን ማለት ነው?››
‹‹አይታይሽም እንዴ…ከልጅነቴ ጀምሮ ሳፈቅራት የኖርኳትን ሴት የሆነ ዘዴ ተጠቅሜ እንድታፈቅረኝና እሺ ብላኝ እንድታገባኝ ማድረግ ካልቻልኩ እንዴት ነው ሌላ ሰውን ማገዝ የምችለው…ይሄው ለሁለተኛ ጊዜ አጣኋት …ያሁን ማጣት ደግሞ ይግባኝ የሌለው ነው…እራሴንም ሰዎችንም እያጭበረበርኩ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ፡፡›› ‹‹አይ..ያ እውነት አይደለም…ቤተሰቦቼን ምን ያህል እንዳገዝካቸው እኔ ነኝ ማውቀው..አረ የእነሱን ተወውና እኔን እራሱ በስልክ ብቻ በምታወራኝ ምን ያህል ጥንካሬና ብርታት እንደምትሰጠኝ አታውቅም..ፈፅሞ በምንም ምክንያት ተስፋ መቁረጥ የለብህም..ደግሞ አንድ ግንኙነት አልተሳካምና ጠቅላላ ያንተ ህይወት አበቃለት

ከመጽሐፍት መንደር💠

04 Feb, 17:50


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያሁለት

ባልና ሚስቶቹን ቤታቸው ወስዶ እንደጣላቸው ቀጥታ የመኪናውን መሪ ወደአስቴር ቢሮ ነው የጠመዘዘው…ገብቶ ምሳ እንዲበላ ቢለምኑት እንኳን እሺ አላለቸውም፡፡እንደሚመጣ አልነገራትም ቀጥታ ከቢሮዋ ፊት ለፊት አቆመና ደወለ
‹‹ሄሎ ወንድሜ….እንዴት ነው ቢሾፍቱ በጣም ተመችታሀለች መሰለኝ?፡፡››
‹‹መጥቻለው….ምሳ አትጋብዢኝም?፡፡››
‹‹የእውነት መጣህ?››
‹‹አዎ ቢሮሽ ፊት ፊት መኪናዬን አቁሜያለው፡፡››
‹‹በቃ መጣሁ››ብላ ስልኩን ዘጋች….5 ደቂቃ ነው ያስጠበቀችው፡፡ገና የቢሮዋን የህንፃ ደረጃ ስትወርድ ጀምሮ ነው አይኑ ውስጥ የገባችው…ሙሉ ሮዝ ቀለም ያለው ጉረድ ቀሚስና ኮት ለብሳለች…ፀጉሯ ወደኃላዋ ትከሻዋ ላይ እንዲተኛ ተደርጎል…ውብ ሆናለች….መኪናዋን ስለምታውቃት ብዙም ሳትደነጋገር ቀጥታ ወደእሱ ነው ያመራችው…ይህቺ ሴት እህቱ እንድትሆን አይደለም የሚፈልገው…ጓደኛም እንድትሆነው አይደለም…የፍቅር አጋሩ ሚስቱ ሊያደርጋት ነው ምኞቱ..ይሄ ምኞቱ ደግሞ አሁን በቅርብ በውስጡ የበቀለ ስላልሆነ ህመሙ ቀላል አይደለም…ገና አፍ ፈቶ በኮልታፋ አንደበት መንተባተብ በጀመረበት በጮርቃነት እድሜው ጀመሮ እሷ ሚስቱ እንደሆነች ያስብ ነበር፣እርግጥ በዛን እድሜ ሚስት ማለት እራሱ ትርጉሙ ምን ማለት አንደሆነ አያውቅም ነበር፣ቢሆንም ጭላንጭል የሆነ ግንዛቤ ነበረው…ሚስት ማለት አንድ ክፍል ውስጥ አንድ አልጋ ላይ ሁሌ አብራ

የምትተኛ ሴት እንደሆነች ከአባትና ከእናቱ ግንኙነት መረዳት በቻለበት ጊዜ ነው፣ከእሱ ጋር ለዘላለም መተኛት ያለባት ሴት አስቴር እንደሆነች ወስኖ የነበረው፣በዛን የልጅነት ጊዜ እናቷ የቤታቸውን እንጀራ ልትጋግር ስትመጣ አስከትላት ስትመጣ ጀምሮ እዛው እሷን ማስቀረት ምኞቱ ነበር…እና ያ ምኞት ግለቱን ጠብቆ እየፋመ ነበር የቀጠለው…
ጊዜው ሲደርስ ግን ነገሮች ቀደም ብሎ እንዳሰባቸው ቀላል አልነበሩም…ገቢናውን ከፈተላት ገባች.. ጉንጩን አገላብጣ ሳመችው…ሁል ጊዜ የእሷ መሳም ከሌላው መሳም በጣም ይለይበታል…ወፈር ብሎ ወደፊት ግልብጥ ያለው ፍም ከንፈሯ ሰውነቱ ላይ ሲርፍ የተለየ ሙቀት ነው ሰውነቱ የሚያመነጨው…ልክ የጋለ ቢላዋ አካል ላይ ሲያርፍ የሚሰማው አይነት ትሽሽሽ..የሚል የማቃጠል የመለብለብና የመላጠ ስሜት……
‹‹አንተ ወፍረህ ነው የመጣሀው….ስራ ላይ ነበርክ ወይስ ጫጉላ ሽርሽር ላይ?››
‹‹በይው…አንቺም ተመችቶሻል…ምሳ የት አንብላ?››
‹‹ወደ እኔ ቤት ንዳው››
‹‹ምነው ከሰዓት ስራ የለሽም እንዴ?››
‹‹ዛሬ ቅዳሜ እኮ ነው…ግማሽ ቀን ነው የምንሰራው››
‹‹እና አራበሽም ..በልተን ብንሄድ አይሻልም?››
‹‹አይ ሰራተኛዬ አዘጋጅታ እየጠበቀችን ነው…ዘና ብለን ቤታችን ብንበላ ይሻላል….ወንድሜ ስለመጣህ ደስ ብሎኛል››
‹‹እኔም ከሰዓት ስራ ስለሌለሽ ደስ ብሎኛል››ብሎ መኪናዋን ወደ አስፓልት መሀል አስገባና ነዳት….የእውነትም ከሰዓት ስራ የለኝም ብላ ወደቤቷ ይዛው እየሄደች በመሆኑ ከፍተኛ ደስታ ተስምቶታል…ከአመታት በኃላ መልሶ ዛሬ እድሉን ይሞክራል፡፡አዎ በስደት ከሄደበት ባእድ ሀገር ተመልሶ የመጣውም ለዚሁ ነው፡፡ከባሎ እንደተለያየችና እሱም በዛ ንዴት ከሀገር ውጭ መሰደዱን ሲሰማ ነው ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ የመጣው…አንሆ ተመልሶ በመጣበት ባለፉት ስድስት ወሮች እሷን ከገባችበት ድባቴ እንድትወጣና ያልተሳካ ትዳሯ ከፈጠረባትን የስነልቦና መሰበር እንድታገግም እንደወንድም እንደ ጓደኛም ከዛም አልፎ እንደባለሞያም  ከጎኗ  ሆኖ  ሲያግዛትና  ሲደግፋት  ነበር…አሁን  ግን  ልቧ  ሌላ  ፍቅር

ለማስተናገድ ዝግጁ ነው ብሎ ያስባል..በዛ ላይ የእሱ እና የእሷ ፍቅር አዲስ ዛሬ የበቀላ ሳይሆን ድሮ በየሁለቱም ልብ ተዳፍኖ ያለ ነው…አሁን ያንን መቆስቆስና መልሶ እንዲቀጣጠል ትንሽ የፍቅር ቤንዚል ማርከፍከፍ ነው…ለዚህ ድርጊት ያበረታታው ሰሞኑን ያየው በአቶ ሃይለልኡል እና በወ.ሮ ስንዱ መካከል የተከሰተው የፍቅር ግርሻ ነው፡፡
‹‹አዎ…አስቴርን አገባታለሁ…ከበፊት ባሏ የወለደችውን አንድ ልጅም እንደልጄ አድርጌ አሳድገዋለው››በውስጡ አልጎመጎመ…‹‹እና በቅርብ ቀን እሷም ወንድሜ የምትለውን ጥሪ ትተውና ባሌ ብላ ትጠራኛለች…ልጇም አጎቴ ብሎ የሚጠራውን አቁሞ አባቴ እንዲለኝ
አደርጋለው››ይሄንን ስላሰበ ብቻ ውስጡ በደስታ ተፍነከነከ..ቤት ሲደርሱ እውነትም እንዳለችው ቆንጆ ምሳ ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው፡፡እየተጎራረሱ በሉ፡፡ከምግብ በኃላ ብና ተፈላላቸው..እሷ ሁለት ሲኒ እሱ አንድ ሲና ጠጡና ተጠናቀቀ፡፡
‹‹እዚሁ ልንገራት ወይስ ይዣት ወጣ ልበልና ዘና ያለ ቦታ ወስጄ ዘና ባለ ስሜት ላይ ከሆነች በኃላ ልንገራት ››እያለ ሲወዛገብ ቆየና‹‹እ…ፕሮግራማችን እንዴት ነው….?ወጣ እንበል ወይስ እዚሁ ነው የምንቆየው?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አይ…ወጣ እንላለን..ሱፐርማርኬት ወጥቼ መሸማመት አለብኝ..መጠነኛ ድግስ ደግሳለው፣ማታ እንግዳ አለብኝ››
ንግግሯ ግራ አጋባውም.. ደነገጠም፡፡
‹‹የማታ እንግዳ ምን አይነት ነው?›› our
‹‹አንተም አለህበት…ዛሬ እዚህ ነው አይደል የምታድረው?››
እሷ ጋር እንዲያድር ስለጠየቀችው ደስ ብሏታል ..ግን እንግዳውስ…?ለመሆኑ ማን ነው
…?ሴት ነው ወንድ?፡፡‹‹እሺ ..እዚህ ነው የማድረው…ግን እንግዳውስ?››
‹‹እንግዲህ እሱን ከመጣ በኃላ ነው የምናውቀው…ልደር ካለ ግን እምቢ ማደር አትችልም የምለው አይነት ሰው አይደለም››በማለት ግራ አጋቢ መልስ ሰጠችው፡፡መልሷ ይብልጥ ቁርጠት ለቀቀበት…ይሄኔ ከመስሪያ ቤቷ ባለደረቦች አንዱ ነው….ሀለቃዋ ይሆን እንዴ…?ቢሆንስ ልደር ስላለ እንዴት እሺ ልትለው ትችላለች..?››ወይ ሴቶች ምን አይነት ቅኔ የሆኑ ፍጡሮች እንደሆኑ ሁሌ እንደደነቀው ነው፡፡ወንድም ሴትም በአንድ ላይ ሰው ተብሎ

መፈረጁ  አግባብ  አይደለም….አስተሳሰባችን  እምነትና  ፍላጎታችን  ምኑም  እኮ አይገናኝም››ሲል በውስጡ አብሰለሰለና..ነገሮች እስኪደርሱ ጠብቆ ለማየት ወሰነ…
‹‹ከዛ በፊ የተመቻቸ ጊዜ ካገኘው ነግራታለሁ…እንደውም ከማታው ፕሮግራሞ በፊት የእኔን ሀሳብ መስማት አለባት››የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ‹‹በቃ እንሂዳ››አላት፡፡
‹‹እሺ፣ተነስ ብላ ቦርሳዋን አንጠለጠለችና ተነሳች..ተያይዘው ወጡ ..ያለችው ሱፐር ማርኬት ይዛው ከገባች በኃላ ምትፈልገውን ነገሮች ሁሉ ተገዝተው በመኪናው ከተጫኑ በኃላ.. ማኪያቶ እንጠጣ ብሎ አንድ ፀጥተኛ ካፌ ይዞት ገባና..ፊት ለፊት እንደተቀመጡ እንደምንም እራሱን አጠንክሮ ወደነጥብ መንደርደር ጀመረ
‹‹ለምን ወደውጭ እንደሄድኩ ታውቂያለሽ አይደል?››
‹‹ሁለተኛ ዲግሪህን ለመማር ነዋ››
‹‹አይ ያማ ሽፋን ነው….እውነተኛ ምክንያቴን አንቺም በደንብ ታውቂዋለሽ..ወደውጭ የሄድኩት ባንቺ ተበሳጭቼ ነው፡፡››
‹‹አንተን ለማበሳጨት ብዬ ግን ምንም ያደረኩት ነገር የለም››
‹‹እሱን ማግባት አልነበረብሽም››
‹‹ለምን …ታዲያ አንተን ወንድሜን ማግባት ነበረብኝ?››
‹‹ምን ችግር አለው?እርግጥ እንደወንድምና እህት አንድቤት አድገናል..ግን የስጋ ትስስር አልነበረንም›

ከመጽሐፍት መንደር💠

02 Feb, 17:34


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያአንድ

ተካ አቶ ኃይለልኡል ባዘዙት መሰረት ሽጉጡን ሙሉ ጥይት ሞልቶ ወገቡ ላይ ከሸጎጠ በኃላ አጉሊ መሳሪያ ያዘና  ማንን ሳያስከትል ቀጥታ መኪና ውስጥ ገብቶ ወደ ቃሊቲ ነዳው….የሰውዬውን ጥርጣሬ ምንም አልተዋጠለትም…‹‹ልጅቷ ስንት አማራጭ እያላት እንዴት እዛ ጭንቁርቁስ ቤት ከጭርቁስቁስ ሰዎች ጋር ለመቆየት ታስባለች? ››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡ ሊዋጥለት አልቻም…፡፡

በፀሎት ከጠፋችበት ቀን አንስቶ በመላ ሀገሪቱ ፍላጋ የተሰማሩትን በመቶ የሚቆጠሩ ግለሰቦችን የሚመራው ..መረጃ የሚቀበለው አዲስ ቦታ ስምሪት የሚሰጠው እሱ ነው፡፡እና የእሱ እቅድ የሆነ ቦታ መኖሯን በሆነ መንገድ ቀድሞ ቢደርስበት እንደምንም ብሎ የራሱ ሰው በሚስጥር እንዲያገኛት አድርጎ በእጅ አዙር 5 ሚሊዬኑን የሽልማት ገንዘብ ለመቀባበል አቅዶ ከልቡ እየሰራ ነበር...እርግጥ እንደዚህ እያደረገ መሆኑን ቀድመው ቢደርሱበት ያለምንም ማቅማማት ግንባሩን በጥይት እንደሚነድሉት እርግጠኛ ነው…ግን በህይወት የተሻለ ነገር ማግኘት ሪስክ መውሰድ የግድ እንደሆነ የሚያምን ስለሆነ ነገሩን ልክ እንደቁማር ነው ያየው..‹‹ወይ በላለሁ..ወይ ደግሞ እበላለው››ብሎ ነበር ውሳኔ ላይ ደርሶ በተግባር ሲንቀሳቀስ የከረመው፡፡…አሁን ሰውዬው እንደሚሉት ልጅቷ የገመቱት ቦታ የምትገኝ ከሆነ ያ ሁ እቅዱ ውሀ በላው ማለት ነው፡፡ቦታውን ራሳቸው ቀድመው አውቀው ስለነገሩት ሽልማት የሚሰጡበት ምንም ምክንያት የለም….መኪናውን ወደእዛ ሲያሽከረክር በውስጡ በፀሎት የተባለው ቤት በፍፅም እንዳትገኝ እየፀለየ ነበር፡፡እንደደረሰ ከመንገድ ማዶ አስፓልት ጠርዝ ላይ መኪናውን ፓርክ አደረገና የመኪናው መስኮት በከፊል ከፍቶ ማጊሊያ መነፅሩን ወደእነ አቶ ለሜቻ ግቢ አነጣጠረና ገቢ ወጪውን መመልከትና በመሀከልም የተለየ ነገር ያገኘ ሲመስለው በሞባይሉ ፎቶ ማንሳት ጀመረ…
ስራ የጀመረው ከጥዋቱ 5 ሰዓት አካባቢ ቢሆንም እሰከ 10 ሰዓት ሁለት ሶስት ጊዜ አሮጊት ሴት ስትወጣ ስትገባ ከማየት ውጭ በግቢው ውስጥ አይን የሚስብ ምንም አይነት እንቅስቃሴ አልነበረም…ሰዓቱ እየረዘመ ሲሄድ ተስፋ እየቆረጠና እየተሰላቸ መጣ…ለዛሬ ይበቃኛል ብሎ 11 ሰዓት ላይ አካባቢውን ለቆ ወደቤቱ ሄደ ..
በማግስቱ በጥዋት ማለዳ አንድ ሰዓት ላይ ነበር የመጣው፣እና ሁለት ሰዓት ላይ የሚፈልገውን አገኘ ..ደጋግሞ ፎቶ አነሳው…በቤቱ አንድ ሴት ልጅ ብቻ እንዳላቸው አጣርቷል ..አሁን እየገቡ እየወጡ ያሉት ግን በተቀራራቢ እድሜ ላይ የሚገኙ ሁለት ወጣቶች ናቸው፡፡አንደኛዋ የቤቱ ልጅ እንደሆነች እርግጠኛ ነው…ሁለተኛዋ ግን የሚፈልጋት የባለፀጋው ቅምጥል ልጅ ትሁን አትሁን መለየት አልቻለም…የለበሰችው ልብስ የተለመደ አይነት ነው..በዛ ላይ ፊቷን ጭንቅላቷን ጭምር በሻርፕ ሸፍናለች…ዝም ብሎ ከመኪናው በመውረድና በእግሩ ወደ አጥሩ በመጠጋት ከቅርብ ርቀት በርከት ያለ ፎቶ አነሳና ለአቶ ኃይለ ልኡል ላከላቸው፡፡

አቶ ኃይለልኡል በዚህ ጊዜ ከባለቤታቸው ጋር በሰለሞን በሚሾፈር መኪና ከቢሾፍቱ ወደአዲስ አበባ እየተመለሱ ነበር፡፡ስልካቸው ድምፅ ሲያሰማ ከኪሳቸው አወጡና ተመለከቱት..መልዕክት መሆኑን ሲያዩ ከፈቱት…አይናቸው ተጉረጠረጠ….
‹‹እራሷ ነች ..ልጄ እራሷ ነች….ከጎናቸው ያለችው ሚሳታቸው ላይ ተጠመጠሙና ጉንጮቾን አገላብጠው ይስሙ ጀመር››
‹‹እንዴ ኃይሌ ምን ተፈጠረ..?ምን ተገኘ..አረ ንገረኝ?››
‹‹ይሄውልሽ..እንቺ እይው..ፊቷን ብትሸፋፈንም እራሷ ነች፡፡››ወይዘሮ ስንዱ ስልኩን ከባላቸው እጅ ተቀበሉና አፍጥጠው ተመለከቱ…..ከባላቸው በበለጠ በመደነቅ ኡኡ.አሉ…መኪናዋን በእልልታ አደባላለቁት…ሰለሞን የነገሩ ውል ስላልገባው መሪውን ጠመዘዘና የመንገዱን ዳር አስይዞ መኪናዋን አቆማት…በራፉን ከፍተው ወረዱ….እሱም ተከትሏቸው ወረደ‹‹አረ ለእኔም ንገሩኝ ምንድነው? እንዲህ የሚያስፈነጥዝ ደስታ፡፡››
‹‹ልጃችን የት እንዳለች አወቅን..እያት ተመልከት››ስልኩን ከሚስታቸው ተቀበሉና ለሰለሞን አቀበሉት..አንድ ፊቷ በቅጡ የማይታይ ወጣት ፎቶ ነው…ግን በፀሎት እንደሆነች ወዲያው ነው ያወቃት..ሙሉ ፊቷን ሳያይ እሷ እንደሆነች አንዴት እንዳወቀ አልገባውም…››
‹‹አየህ …ልጃችን እራሷ ነች…ሰው እንዳይለያት ነው ፊቷን የሸፋፈነችው……››
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለችው?››ጠየቀ ሰሎሞን፡፡
‹‹የት እዳለች ቆይ ነግራችኃላው››ብለው ስልኩን ተቀበሉና ደወሉ
‹‹ሄሎ….ፎቶው ደርሶኛል፡፡››
‹‹አዎ ሳስበው እሷ ትመስለኛለች››
‹‹አዎ እሷ እራሷነች…ከቦታው እንዳትንቀሳቀስ..እዛው ጠብቀን…ከቢሾፍቱ እየተመለስን ስለሆነ ከ15 ደቂቃ በኃላ ያለህበት እንደርሳለን››
‹‹ወጥታ ከሄደችስ…?ላስቁማት››
‹‹አይ..ልጄን ቀጥታ እኔው ነኝ የማገኛት..እንዳታስቆማት ትደነግጥብኛለች…ከቤት ከወጣች ዝም ብለህ በርቀት እየተከታተልክ ያለችበትን ታሳውቀኛለህ፡››

‹‹እሺ..ጌታዬ እንዳሉት አደርጋለው››
‹‹ጎበዝ ..እንዳስደሰትከኝ አስደስትሀለው…ቆንጆ ጉርሻ ይጠብቅሀል ››
‹‹እሺ ጌታዬ››ስልኩን ዘጉና‹‹በሉ ጊዜ አናባክን ..ግቡና እንሂድ››
‹‹እንዴ የት አንዳለች ንገረን እንጂ……?››ወ.ሮ ስንዱ ጠየቁ
‹‹ስንድ ልጃችን ሰዎቹ ጋር ነው ያለችው….››
‹‹የትኞቹ ሰዎች››
‹‹እነአቶ ለሜቻ ጋር..ማለቴ የልብ ለጋሾ ቤተሰብ ጋር ነው ያለችው››
‹‹ወይ ጉዴ….አሁን ምንድነው የምናደርገው?››እያሉ ወደመኪናው ገቡ፡፡ አቶ ኃይለልኡልም ተከትለዋቸው ገቡ….ሰለሞን በሰማው ያልተጠበቀ ነገር ግራ እንደተጋባና ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰላሰለ ገቢና ገባ፡፡ መኪናውን አንቀሳቀሳት…ባልና ሚስቶቹ በደስታ ሰክረው እሱን ከቁብ ሳይቆጥሩት እርስ በርስ በፈንጠዝያ ሲጎሻሸምና ሲሳሳሙ እሱ ምን ማድረግ እንዳለበትና ይሄንን ያለጊዜው ያጋጠመውን ነገር እንዴት እንደሚፈታ እያሰላሰለ ነበር የሚነዳው….
አቃቂ አቶ ለሜቻ ቤት ለመድረስ 500 ሜትር ያህል ሲቀራቸው የመኪናውን መሪ ወደግራ ጠመዘዘና ፊት ለፊት ከሚታየው ሆቴል ይዞቸው ገባ..ባልና ሚስቶቹ በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ
‹‹ሰለሞን…ምን እያደረክ ነው?››አቶ ኃይለልኡል ጠየቁ፡፡
‹መነጋገር አለብን››
‹‹ስለምን?››
‹‹አሁን ልጃቹህ ጋር ከመሄዳችሁ በፊት አረፍ ብለን መነጋገር አለብን››
‹‹ምን መነጋገር ያስፈልጋል…?በቃ እኔና እናቷ ሄደን ልጃችንን ወደቤት ይዘን እንሄዳለን….እንደምታየው  አሁን  ሁሉ  ነገር  ውብ  እና  የተስተካለከለ  ነው..አይዞህ

አታስብ…ከንተጋር  ያለንን  ነገር  እንቀጥላለን..ከሶስት  ቀን  በኃላም  ወደአልከው  ቦታ ትወስደናለህ››
መኪናውን  አቆመና  ሞተሩን  አጥፍቶ  ወደኃላ  ዞረ..ፊት  ለፊት  እያያቸው‹‹ይሄ  ነገር እንደምታስብት ቀላል ይመስላችኃላ?››
‹‹ማለት?››
‹‹አሁን ያለችበት ቤት ሄደችሁ በማንኳኳት..ነይ ልጄ በቃ አግኝተንሻል አሁን ወደቤትሽ ተመለሺ ብትሏት ..እሺ ብላ በደስታ ዘላ የምትጠመጠምባችሁ ይመስላችኃላ…እምቢ መሄድ አልፈልግም ብትል ምን ታደርጋላችሁ ?በግድ በጎረምሳ አሳዝላችሁ መኪና ውስጥ በመክተት ወደቤት ትወስዷታላችሁ….?ከዛስ..?አንድ ክፍል ውስጥ ቆልፋችሁባት በራፍ ላይ ሁለት ጠብደል ጠባቂ ታቆማላችሁ?እስኪ ንገሩኝ ምንድነው የምደርጉት?› በድንጋጤ እርስ በርስ ተያዩ‹‹በእውነት እምቢ ብትለን ምንድነው የምናደርገው?›ወ.ሮ ስንዱ በተሰበረ ድምፅ ባላቸውን ጠየቁ፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

30 Jan, 16:45


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሀያ

‹‹አግብተሀል እንዴ?››
ድንገት ከርዕሳቸው ውጭ የሆነ ጥያቄ ስለጠየቁት ድንግርግር አለው፡፡
‹‹ለምን መሰለህ የጠየቅኩህ..?እንዲሁ ሳስበው አንተን ያገባች ሴት በጣም እድለኛ ትመስለኛለች….፡፡››
‹‹ምን አልባት ልትሆን ትችላለች ..እስከአሁን ግን አለገባሁምም አረ እንደውም ፍቅረኛም የለኝም››
ፈገግ አሉ….‹‹ሸክላ ሰሪ በገል ይበላልል›› አሉ…ብዙ ማወቅም እኮ መጥፎ ነው››
‹‹እንዴት?››
‹‹የምትፈልገውን ሁሉ የምታሟላ ሴት ለማግኘት በጣም ይከብድሀላ…ሁሉን ነገር አሟልታ ጥንቅቅ ያለች ሴት አታገኝም..በዛ እርግጠኛ ሆኜ ልነግርህ እችላለው…ግን ምትወድህና ምትወዳት ልጅ ሆና እራሷን ለመለወጥና ለማሻሻል የምትጥር ከሆነ በቂ ነው…አንተ ጎበዝ አንደበተ ርትኡ ባለሞያ ስለሆንክ መስመር ታስይዛታለህ››
እንዴት ብሎ መምከሩን ትቶ ተመካሪ እንደሆነ አልገባውም፡፡‹‹እሺ…የእናንተን ጉዳይ ከዳር ካደረስኩ በኃላ አስብበታለው….ምን አልባት እናንተ ትሆናላችሁ የምትድሩኝ…››
‹‹ለዛውም ድል ባለ ድግስ ነዋ››

‹‹እሺ..አሁን ይበቃናል…የምሳ ሰዓት ስለደረሰ ወደሳሎን እንሂድ››
‹‹አዎ ..ይበቃናል..ይሄኔ ኃይሌ ብቻውን ደብሮታል››
ፈገግ እለ ….. ከመቀመጫው ተነሳና ወደውጭ መራመድ ጀመረ…ወ.ሮ ስንዱም ተከተሉት፡፡


ከሳምንት በኃላ……..
በቢሾፍቱ ቆይታቸው በባልና ሚስቶቹ መካከል አስገራሚ የሚባል ለውጥ ነው የታየው፡፡ቢያንስ እረስ በርስ በመሀከላቸው ያለ ንግግር የጥሩ ጓደኛሞች መምሰል ከጀመረ ሰነባብቷል…ይሄ ለውጥ ሰለሞንን ይበልጥ እንዲበረታታ እና ሙሉ ኃይሉን ስራው ላይ እንዲያውል አግዞታል፡፡
‹‹እንግዲህ ዛሬ የመጨረሻ ቀናችን ነው ነገ ወደአዲስአባ እንመለሳለን…ሶስት ቀን እረፍት እንወስድና ምን አልባትም ለመጨረሻ ጊዜ ለሌላ 15 ቀን ወደሌላ መዝናኛ ቦታ እንሄዳለን፡፡በቀጣይ የምንሄድበት ከዚህ የተለየ ነው…ሌሎች ሰዎች ማለቴ ጎብኚዎች የሚኖሩበት ቦታ ነው…እዛ ምንሄደው ነፃ ሆናችሁ እንድትዝናኑ ነው..እኔም አብሬያችሁ ኖራለው ግን ነፃ ናችሁ…እዚህ እንዳለው ብዙ ማዕቀብና እገዳ የለም…ስልካችሁን እንደፈለጋችሁ መጠቀም ትችላላችሁ.ሰሻል ሚዲያ ቴሌቪዝን ማየት ትችላላችሁ …ከሰው መተዋወቅና መገባበዝ ትችላላችሁ..አንድ ማትችሉት ነገር መለያየት ብቻ ነው….ለ15 ቀን የምታደርጉትን ሁሉ አብራችሁ ታደርጋላችሁ..››
‹‹ገባን ..ያልከው 15 ቀን የመጨረሻችን ይመስለኛል››
አዎ እኔም እንደዛ ነው የማስበው..በእውነት እዚህ ባሳለፍነው 15 ቀን ሁለታችሁም ካሰብኩት በላይ ከፍተኛ ጥረት አድርጋችኃል …እናም ትልቅ ለውጥ እንዳመጣችሁም ይሰማኛል…እናንሰትስ ምን ይሰማችኃል…?አቶ ኃይለልኡል እስኪ ከእርሶ ልጀምር፡፡

‹‹እኔ በጣም ደስተኛ ነኝ…እስከዛሬ ሚሲቴን ብቻ የምበድል መስሎ ነበር የሚሰማኝ ለካ ልጄንም ራሴንም ጭምር ነበር እያሰቃየው የነበረው….እውነት አንተና ልጄ የእድሜ ልክ ባለውለታዎቼ ናችሁ››
ፊቱን ወደወ.ሮ ስንዱ ዞረና ተመሳሳዩን ጥያቄ ጠየቃቸው፡፡
‹‹አዎ…ኃይሌ እንዳለው ደስተኛ ነን…በፊት ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጌ ገዳም ገብቼ መመልኮስ ነበር ምኞቴ ..ምክንያቱም ህይወት አስጠልታኝ ነበር…ቤቴም ኑሮዬም ይቀፈኝ ነበር…ጨለማ የሆነ ሀዘን ውስጥ ገብቼ ነበር..አንድ ያለችኝ አስደሳች ነገር ልጄ ብቼ ነበረች
..እሷም ከጠፋች በኃላ ደግሞ ነገሮች ለእኔ ምን ያህል አስቸጋሪ እንደሚሆኑ መገመት ቀላል ነው…አሁን ግን እንደዛ አይደለም የሚሰማኝ….ደግመኛ እንደመወለድ አይነት የመታደስ ስሜት እየተሰማኝ ነው…የመከራና የሀዘን ቆዳዬን ከላዬ ገፍፌ ጥዬ በአዲስ ተስፋና ፍቅር ተወልጄለሁ..አሁን ቤቴም ባሌም ይናፍቁኛል….ሃይሌን ከዚህ በፊት ለሆነው ሁሉ ይቅር ባዬዋለሁ.. እሱም ይቅር እንደለኝ ገምታለው፡፡››
ኃይለልኡል ተፈናጥረው ከመቀመጫቸው ተነሱና ሚስታቸው ላይ ተጠመጠሙ…ሁለቱም ተቃቅፈው መላቀስ ሲጀምሩ….ሰለሞንንም ስሜታዊ አደረጉት፡፡ተላቀው ወደቦታቸው ለመመለስ..ከ10 ደቂቃ በላይ ፈጅቶባቸዋል፡፡
ሰለሞን ንግግሩን ቀጠለ‹‹ጥሩ እንግዲህ… እዚህ ደረጃ ላይ ከደረስን አንዳንድ አጠቃላይ ስለሆኑ ነገሮች እናውራ፡፡ያው እናንተ በጋብቻ ውስጥ ረጅም እድሜ ስለአሰለፋችሁ ከእኔ የበለጠ ልምድ እንዳላችሁ አውቃለሁ....አሁን የማወራው የምታውቁትን ነገር ነው…ላሳውቃችሁ ሳይሆን ላስታውሳችሁ ፈልጌ ነው››
‹‹ጥሩ እየሰማንህ ነው ….ቀጥል››
‹‹እንግዲህ እቤት የባል ብቻ አይደለም፣የሚስትም ብቻ አይደለም፣ እቤት የልጆችም ጭምር ነው።በዚህ ምክንያት ለሁሉም ኑዎሪዎች እኩል ምቹ መሆን አለበት።እናንተ ከአሁን ወዲያ በቤታችሁ የሚዘረጋው ስርአት ህግና የአኗኗር ዘየ..ሶስታችሁን በእኩል ከግምት ያስገባ መሆን አለበት፡፡ሌላው ንብረታችሁን በተመለከተ የእኔ የሚለውን ቃል ከመጠቀም የእኛ የሚለውን የጋራ ቃል መጠቀም የተሻለ ነው።የእኛ ቲቪ..የእኛ ቤት...የእኛ ጊቢ የእኛ ፋብሪካ፣ብሎ የመናገር ልምድ ሊኖራችሁ ይገባል።እያንዳንድ የቤተሰብ አባል የእዛ ቤተሠብ

የአክሰዬን ባለድርሻ ናቸው።ያንን ደግሞ በተግባርም በስነ-ልቦናም መረጋገጥ አለበት።በቤተሰብ ቢዝነስ ውስጥ ስለሚፈጠር ዋና ዋና ክስተት ስለትርፍም ሆነ ኪሳራ ሁሉም ሰው በተገቢው መጠን መረጃ ሊኖረው ይገባል….ሁሉንም ኃላፊነት አንዱ አካል ብቻ ጠቅልሎ መውሰድ የለበትም…እዚህ ላይ በተለይ አቶ ኃይለልኡል ብዙ ነገር ማስተካከል የሚጠበቅቦት ይመስለኛል››
‹‹ገብቶኛል..እሺ…አስተካክላለው፡፡››

‹‹ሌላውና ወሳኙ … የተለየ ችግር ከሌለ በስተቀር ባልና ሚስት መኝታ ክፍላቸውንም ሆነ አልጋቸውን መለየት የለበቸውም…በተጨማሪም ባልና ሚስት በምንም አይነት ሁኔታ ወደመኝታቸው ሲሄድ አኩርፈውና በውስጣቸው ተበሳጭተው ወይ ቂም ይዘው መሆን የለበትም።መኝታ ክፍል ለባለትዳሮች እንደቤተመቅደስ ነው መሆን ያለበት ። የሚሳሳሙበት... የሚተቃቀፉበት.... የሚዋደድበትና የሚፋቀሩበት ….ስለጋብቻቸው እና ስለልጆቻቸው ደህንነትና ሰላም የሚማከሩበትና የሚፀልዩበት የገመና መክተቻ ቦታቸው ነው መሆን ያለበት ። ስለዚህ ... ቅያሜያቸውን ሆነ ቅሬታቸውን ሳሎን ጨርሰው ለጭቅጭቃቸው መፍትሄ አበጅተውለት እና ይቅር ተባብለው ነው በሳቅና በፈገግታ ወደመኝታቸው መሄድ ያለባቸው። አዎ ወደመኝታ ክፍላቸው ሲያመሩ በፍፁም ሰላምና ፍቅርና መሆን አለበት...የበለጠ ለመፍቀር...የበለጠ ለማረፍና ..የበለጠ ለመታደስ ።ይሄ ሁለታችሁንም በእኩል ደረጃ የሚመለከት ጉዳይ ነው፡፡››
ሁቱም አንገታቸውን እላይ እታች በማነቃነቅ መስማማታቸውን ገለፁ ‹‹ሌላው በቤት ውስጥ አንደኛው ሌለኛውን ማገልገል አለበት...ማገልገል ማለት በፍፅም ፍቃደኝነትና ፍላጎት አንደኛው ሌላኛውን መርዳት ማለት ነው።ባል የቤቱ ንጉስ ከሆነ ሚስት ደግሞ ንግስት ነች ማለት ነው ልጆች ደግሞ ልኡላን ናቸው።ማንም ከማንም የበለጠ አስፈላጊ አይደለም...ማንም ከሌላኛው ያነሰ አይደለም።ለቤቱ ሙሉነትና ፍፁምነት ሁሉም የየራሱ ኃላፊነትና ድርሻ አለው።በፍቅርና በጋብቻ ህይወት ውስጥ እርስ በርስ ያለ መከባበር በጣም ወሳኝ ነው።አንድ ለሌላዎ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን ሲኖሩት በትህትና እና ክብር በተሞላ ሁኔታ ጥያቄውን ማቅረብ አለብት።እርስ በርስ ያለ ግንኙነት የማስመስል መሆን የለበትም...እንግዳ ሲኖር የሚደረግ አርቴፊሻል የማስመሰል እንክብክቤ እና አክብሮት

ከመጽሐፍት መንደር💠

29 Jan, 03:24


በነጭ ምዕመናን ታቦቷ ታጀበ
ዲያቆኑ ተነሳ ሊቃችን ወረበ

ጭብጫቦ እልልታው
     ዝማሬው ይበልጣል
ማርያም ማርያም ሲባል
      ስምሽ ይጣፍጣል።

ማርያም

ዮኒ
    ኣታን #yonatoz

ከመጽሐፍት መንደር💠

27 Jan, 18:30


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራዘጠኝ

ሰሎሞን ሁለቱን ባለትዳሮች ፊት ለፊት አስቀምጦ እያወራ ነው፡፡‹‹የፈለገ ጥረት ብናደርግ ለእያንዳንዱ ብሎን የራሱን ትክክለኛ መፍቻ ካልተጠቀምን ልንፈታው አንችልም!! በህይወታችንም ውስጥ ችግሮች ሲያጋጥሙን ተረጋግተን ለችግሩ ትክክለኛ የመፍትሄ ሀሳብ ማስቀመጥና ለተግባራዊነቱ መንቀሳቀስ ካልቻልን እንዲሁ ስንባክን እና በችግሩ ውስጥ ስንዳክር ነው የምንኖረው፡፡ይሄንን በስራ አለም በትክክል እየተገበራችሁ ውጤታማ እንደሆናችሁ አውቃለው…በትዳር ህይወታችሁስ?ዋናው ጥያቄ እሱ ነው፡፡››
አቶ ኃይለልኡል ተቀበሉት‹‹ገብቶናል…እንደምንም ብለን በመሀከላችንን የተፈጠረውን ክፍተት በማስወገድ እና ፍቅራችንን መመለስ እንዳለብን በደንብ ተረድተናል…አዎ እንደምታየውም ጥሩ መሻሻል እያሳየን ይመስለኛል፡፡››
ሰለሞን ቀጠለ‹‹ጥሩ ግን ፍቅር ብቻውን በሰላም ለመኖር በቂ አይደለም፡፡በመሀከላችው ምንም አይነት ጥል የሌለ ጥንዶች በመሀከላቸው ፍቅር እንዳለ እርግጠኛ መሆን አይቻልም…እንደዛውም ዘወትር በነጋ በጣባ የሚጣሉና የሚጨቃጨቁ ጥንዶችም በመሀከላቸው ያለው ፍቅር አልቋል ወይም ቀዝቅዞል ማለት አይደለም….ከዛ ይልቅ እንዴት እርስ በርስ እንደሚግባቡ እና አንዱ የአንዱን ፍላጎት እንዴት እንደሚረዳ አልገባቸውም ማለት ነው፡፡ስለዚህ አሁን መልሳችሁ ማደስ የሚገባችሁ ፍቅራችሁን ብቻ ሳይሆን እርስ በርስ የመግባባት ችሎታችሁንም ጭምር ነው፡፡አንዳችሁ ሌላችሁን በጥልቀት ለመረዳት እስከምን ድረስ ለመጓዝ ትፈቅዳላችሁ?ይሄ ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡››

ወ.ሮ ስንዱ ለመጀመሪያ ጊዜ ተናገሩ‹‹ትክክል ነህ ልጄ… ለፍቀራችን መበላሸት ዋናው ምክንያት እንደውም እርስ በርስ የመግባባት ችሎታችን ስለተበላሸ ነው….እሱም እኔን እኔም እሱን ለመረዳት ምንም የምናደርገው ጥረት አልነበረም…ሁለታችንም እርስ በርስ እንከን ነበር የምፈላለገው….ያንን በደንብ ተረድቼለው፡፡››
‹‹አዎ ይሄ ችግር የእናንተ ብቻ ሳይሆን የአብዛኛው ባለትዳር ችግር ነው…አንድ ሰው በፍቅር ሲወድቅ በመጀመሪያ ስለራሱ ምቾና ደስታ እንጂ ስላፈቀረው ሰው ደህንነት አይደለም የሚጨነቀው…ሁለቱም ተጣማሪዎች በጋብቻ ጥምረት ውስጥ ለእነሱ የሚመች ሰፋ ያለ ግዛት ቶሎ ብሎ ለመያዝ ይጣጣራሉ…ሁለቱም ተመሳሳይ ፍላጎት ስላላቸው ፍትጊያ ይፈጠራል…አንዱ የሌለኛውን ድምበር ማለፍ…ይሄኛው የዛኛውን ቀይ መስመር መደፍጠጥ ይጀምራል……ከሁለት አንዱ በፍጥነት ነቅቶ ወደኃላ በመመለስ መረጋጋት ውስጥ ካልገባ ችግሩ መስመር ይስታል፡፡
እኔ 25፡50፡25 የሚል ፕሪንስፕል አለኝ፡፡በትዳር ውስጥ እሷ(ሚስትዬው) እሱ(ባልዬው) እና እነሱ (ባልና ሚስቶቹ)አሉ፡፡እና ስሜታቸው፤ፍላጎታቸው፤የህይወት አላማቸው ወ.ዘ.ተ ተጠቅልሎ መቶ ፐርሰን ቢሰጠው፡፡እሷ የግሏ ፍላጎት በግሏ የሚያስደስታት ነገር፤ መዝናኛ ቦታ፤ጓደኞች፤ 25 ፐርሰንት ትይዛለች….እሱም ለብቻው 25 ፐርሰንት ይይዛል፡፡50 ፐርሰንቱ ግን የጋራቸው ነው፡፡በጋራ የሚያቅዱበት፤በጋራ የሚሰሩበትና የሚለፉበት ቤት መስራት፤ልጆች መውለድና ማሳደግ…ወዘተ፡፡ሁል ግዜ ተሰፍሮ 25፤50፤25 ላይሆን ይችላል፡፡በተለይ ሴቶች ከእነሱ 25ፐርሰንት 10ሩን ወይም 15 ቱን ቆርሰው ለጋራቸው ያውሉታል…ወንዶች ደግሞ ከሞላ ጎደል አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ከጋራቸው ላይ ቆረስ አደርገው የእነሱን 25 ፐርሰንት 30 እና 40 አንዳንዴም ከ50 በላይ ያደርሱታል..የዛን ጊዜ የጋብቻው ባላንስ ይናጋል፡፡ምሰሶው መነቃነቅ ይጀምራል..እርማት ካልተደረገለት ጋብቸውን እያከሳ ይሄድና መጨረሻ ያከትምለታል፡፡…የምናገረው ግልፅ ነው አይደል››
‹‹አዎ..በጣም ግልፅ ነው፡፡››
‹‹በምሳሌ ይበልጥ ለማስረዳት አንድ ገጠር የምትኖር አክስቴ ከአስር በላይ ባሎች አግብታለች፡፡ግማሹን እነሱ ናቸው የፈቷት ግማሾቹን እራሷ ነች ያደረገችው፡፡ከሁሉም ግን የሳበኝን አንደኛውን ልንገራችሁ፡፡አገባሁት አለች..በጣም ሰላማዊ ..ምንም አይነት ክፉ ነገር ማይናገር…የጠየቅኩትን ሁሉ የሚያሞላልኝ ሰላማዊ ሰው ነበር አለች፡፡በፊት ከለመደቻቸው ተደባባዳቢ እና ተጨቃጫቂ ባሎች ጋር የትኛውም ፀባዩ የሚገጥም

አልነበረም፡፡ግን ብዙም ሳይቆይ ሰለቻት….ሁሉ ነገር ዝም እና ጭጭ ያለ ሆነባት…በቃ ግንኙነታቸው ውስጥ ነፍስ አጣችበት ፡፡አንድ ቀን በለሊት ተነሳና በሬዎቹንና ሞፈር ቀንበሩን ይዞ ወደማሳ ወጣ …ሲሄድ ቁርስም አልሰጠችውም..ምሳም ይዛ መሄድ ቢገባትም አልወሰደችለትም..ጭራሽም አልሰራችም…በጣም የባሰው ነገር ደግሞ የቤቱን እቃ ብረትድስት ፤ሰሀን ፤ብርጭቆ አንድም ሳታስቀር ከቤት ጀምራ የቤቱን መግቢያ ደጃፍ…ወለሉን ጠቅላላ አዝረክርካ እና ሞልታ ኩርሲ ላይ ቀጭ ብላ ትጠብቀው ጀመር ፡፡.
ከዛ መጣ…ከውጭ ጀምሮ ያዝረከረከችውን እቃ አንድ በአንድ ጎንበስ ብሎ እየለቀመ…‹‹እታዋቡ …ሰላም ነሽ….?ምንም አልሆንሺብኝም አይደል….?››እያለ ሁሉንም እቃ ወደመደርደሪያ መልሶ ስሯ ቁጭ ብሎ በልምምጥ ጭንቅላቷን መዳበስ ጀመረ..
ከዛ ይህቺ አክስቴ ምን ብታደርግ ጥሩ ነው‹‹ ብድግ አለችና ሻንጣዋን ይዛ‹‹እንዴት ቁርስ አላበላሁህ ..ምሳ አለመጣሁልህ….ቤቱን እዲህ አዝረክርኬ ነው የጠበቅኩህ..ምን እስካደርግህ ነው የምትጠብቀው…?ምንም አይነት የወንድነት ወኔ የለህም እንዴ…?ሁለት ሴት አንድ ቤት አይኖርም… ነውር ነው››ብላ ጥላው ወጣች..በዛው ፈታችው ፡፡አያችሁ ትዳር በጣም ውስብስብ ግንኙነት ነው፡፡የበዛ ጭቅጭና ጥል ብቻ ሳይሆን የበዛ ሰላምና ፀጥታም ሊያፈርሰው ይችላል፡፡፡ዋናው በሁሉም ነገር ሚዛን ጠብቆ መጓዝን መልመድ ነው፡፡››
የተወሰነ ትንፋሽ ወሰደና ፊትለፊቱ ካለ የታሸገ ውሀ በማንሳት አንዴ ተጎንጭቶለት ከንፈሩን አረጣጠበና ንግግሩን ቀጠለ፣እነሱም ልክ በቅርብ ፈተና እንደደረሰበት ቸካይ ታማሪ በጥሞናና በትኩረት እየተከታተሉት ነው‹‹አሁን ልብ በሉ፣ ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደለም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቅ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው.. በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ነገር ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር ለብንም፡፡እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራችን ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ጋና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ለዘሬው ይበቃናል…አሁን ወደመናፈሻው እንሂድና ትንሽ ዘና

ከመጽሐፍት መንደር💠

25 Jan, 18:48


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራስምንት

ሰለሞንና በፀሎት በስልክ እያወሩ ነው፡፡
‹‹ለመሆኑ የት ነው ያለሽው?››ሲል ጠየቃት
‹‹ምነው ጠየቅከኝ?››
‹‹አይ ..እንዲሁ ደህንነትሽ አሳስቦኝ ነው….ምን አልባት የማይመች ቦታ ካለሽ ልረዳሽ እችላለው፡፡››
‹‹ምነው ወደቤትህ ወስደህ ደብቀህ ልታኖረኝ አሰብክ››

‹‹ምነው ..ችግር አለው.?.የእውነት የማይመች ቦታ ካለሽ ንገሪኝ››
‹‹አሁን ካለሁበት ቦታ የተሻለ ሊመቸኝ የሚችለው ምን አልባት ገነት ነው….እሱንም ደግሞ ስላላየሁት እርግጠኛ አይደለሁም››
‹‹እንዴ…ከእናትና  አባትሽም  ቤት  የተሻለ  ቦታ  ነኝ  ነው  የምትይኝ…ይሄንን  ማመን አልችልም፡ ››
‹‹ነገርኩህ እኮ…››
‹‹‹እ ..ገባኝ››
‹‹ምኑ ነው የገባህ?››
‹‹ከእናትና አባት ቤት በበለጠ የሚመች ቦታ የፍቅረኛ ቤት ነው››
‹‹በጣም ተሳስተሀል..አዲስ ቤተሰብ አግኝቼለሁ…አራት ናቸው..ሽማግሌ አባትና እናት፣አንድ ዋንድ ሴትና ወንድ ልጅ አላቸው..ሀለት ክፍል ሰርቢስ ውስጥ ነው የሚኖሩት፣ኑሮቸው ከእጅ ወደአፍ ነው… ፍቅራቸው ግን ሞልቶ የፈሰሰ ነው….ለዘላለም ልጃቸው አድርገው ተቀብለውኛል…ከአሁን ወዲህ ባለው ህይወቴ ሙሉ አነሱ ወላጆቼ እና ቤተሰቦቼ እንደሆኑ እንዲቀጥሉ ምንም ነገር አደርጋለው››
‹‹የሚገርም ነው….እናትና አባትሽ ይሄንን ንግግርሽን ቢሰሙ ልባቸው የሚሰበር ይመስለኛል፡፡››
‹‹እንግዲህ ምንም ማድረግ አልችልም…በእነሱ ስህተት ነው ከቤት የወጣሁትና እነሱን ያገኘሁት…አሁን አግኝቼ በደንብ አጣጥሜቸዋለው…እና ወደቤት ብመለስ እንኳን ወላጆቼን ከእነሱ ጋር ነው ማነፃፅራቸው…እና ለእነሱ ቀላል የሚሆንላቸው አይመስለኝም››
‹‹….ለመሆኑ ማንነትሽን ያውቃሉ?›
‹‹አይ አያውቁም.. እኔ ለእነሱ እናቷ የሞተችባት እና የእንጀራ አባቷ ሰክሮ በለሊት ሊደፍራት ሲል አምልጣ የወጣች ሚስኪን ሴት ነኝ››
‹‹ይሄንን ታሪክ አንቺ ነሽ የፈጠርሽው?››

‹‹አዎ…..››
‹‹የምትገርሚ ልጅ ነሽ ..እኔጋም መጥተሸ ተመሳሳይ ታሪክ ብትነግሪኝ አምኜ ልረዳሽ መሞከሬ አይቀርም ነበር››
‹‹የእነሱ እኮ መርዳት አይደለም….እናትና አባት መሆን ነው…..እንደልጃቸው መቀበል››
‹‹ የእውነት አዲሶቹን ቤተሰቦችሽን እኔ እራሱ ለመተዋወቅ ጓጓሁ› ›
‹‹መጓጓትህ ትክክል ነህ››
‹‹ነገሮች ከተስተካከሉ በኃላ ታስዋውቂኛለሽ ብዬ ገምታለው››
‹‹መጀመሪያ እስኪ እኛ ለመተዋወቅ ያብቃን››
‹‹እንዴ እኛኮ በደንብ ተዋወቅን፣ለአመታት የማውቅሽ እንደሆነ ነው የሚሰማኝ››
‹‹እሱስ እውነትህን ነው..ያው አካል ለአካል አልተገናኘንም ብዬ ነው፡፡››
‹‹ባክሽ የስልኬ ጋላሪ ባንቺ  ፎቶዎ ተጨናንቆል  ››ብሎ ያልጠበቀችውን አስደንጋጭ ነገር ነገራት፡፡
‹‹እንዴ በምን ምክንያት?››
‹‹እንዴ ..ደንበኛዬ አይደለሽ?››
‹‹እና የሁሉንም ደንበኞችህን ፎቶ ትሰበስባለህ ማለት ነው?››
‹‹ቆንጆ እና የተለየ የሆኑትን ..አዎ››
‹‹በቻይንኛ ቆንጆ ነሽ እያልከኝ ነው፡፡››
‹‹እ..ምነው አይደለሽም እንዴ?››
‹‹እኔ እንጃ ….ለማንኛውም ደስ የሚል ስሜት እንዲሰማኝ አድርገሀል…እና እኔስ የአንተን ፎቶ የማግኘት መብት ያለኝ አይመስልህም?››

‹‹አይ..አዲሶቹን ቤተሰቦችሽን እንድምታስተዋውቂኝ ቃል ካልገባሽ የምታገኚ አይመስለኝም››
‹‹አዲሶቹን ቤተሰቦቼን….እኔ እንጃ ..ስለምሰስታቸው የማደርገው አይመስለኝም››
‹‹‹ትገርሚያለሽ…፣ዋናዎቹን ቤተሰቦችሽን እኮ ተቆጣጥሬቸዋለው…..ለማንኛውም ይህን የመሰለ ቤተሰብ ስላገኘሽ ደስ ብሎኛል….ይሄውልሽ በህይወት ውስጥ ሶስት አይነት ሰዎች አሉ፡፡ቅጠል የሆኑ ሰዎች… ቅርንጫፍ የሆኑ ሰዎችእና… ስር የሆኑ ሰዎች።ቅጠል የሆኑ ሰዎች ወቅትንና ሁኔታዎችን ጠብቀው ወደ ህይወትሽ የሚገብ ናቸው።ደካሞች ስለሆኑ በእነሱ ተፅዕኖ ስር ፈፅሞ እንዳትወድቂ። ከአንቺ የሚፈልጉትን የሆነ ነገር ስላለ ነው ወደህይወትሽ የሚመጡት... የመከራ ንፍስ በህይወት ዙሪያ ሲነፍስ መርገፍ ይጀምራሉ።እነዚህ ሰዎች አንቺን ማፍቀር የሚቀጥሉት በዙሪያሽ ያሉ ነገሮች ጥሩ እስከሆኑ ጊዜ ብቻ ነው።ንፋስ እንደመታው የወየበ ቅጠል ከላይሽ ላይ ተዘንጥለው ይረግፋሉ። ቅርንጫፍ ሰዎች ደግሞ በአንፃራዊነት ጠንካሮች ናቸው ግን ልትጠነቀቂያቸው ይገባል።ህይወት ጨከን ስትል መገንጠላቸው አይቀርም። ምክንያቱም ጠንከር ያለ የህይወት ጫና የመሸከም አቅም የላቸውም።ነገሮች ጨለምለም ሲሉ እና ተስፋም የሌላቸው ሲመስሉ ጥለውሽ ዞር ለማለት አያመነቱም። ሌሎቹ ልክ እንደአንቺ አዲሶቹ ቤተሰቦች ስር የሆኑ ሰዎች ናቸው። እነዚህ በህይወትሽ በጣም አስፈላጊ ሰዎች ናቸው።ለመታየት ብለው የሚሰሩት ስራ የለም።በመከራሽም በደስታሽም ጊዜ አብረውሽ ናቸው።አስከሞት የታመኑሽ ናቸው።ሲያፈቅሩሽ በነፃ ምንም መልስ ካንቺ ሳይጠብቁ ነው፣እንደዚህ አይነት አንድ ወይም ሁለት ሰው ከጎንሽ ማግኘት የህይወት ዘመን ሽልማት ነው፡፡
‹‹ጥሩ አድርገህ ገልጸኸዋል፡፡እነሱ ብቻ ሳይሆኑ፣አንተም ለእኔ ስር ነህ…በቃ ቸው…ነገ እንደዋወላለን፡፡››
‹‹ቸው …..ደህና ሆኚ››ብሎ ስልኩን ከዘጋ በኃላ …ባለበት ቆሞ ትካዜ ውስጥ ገባ..ይህቺን ልጅ በተመለከተ የተለየ አይነት ኬሚስትሪ በሰውነቱ እየተረጨ ነው….ነገሮች ወዴት እያመሩ ነው?››ሲል እራሱን ጠየቀ፡፡

በማግስቱ……
በፀሎት ከሞላ ጎደል ጤንነቷ እየተመለሰ ነው…አረ እንደውም ድናለች ማለት ይቻላል..የእግሯ ስብራት ሙሉ በሙሉ ተጠግኖ በደንብ መራመድ ችላለች..የፊቷ ቁስለትም ሙሉ በሙሉ ጠጓል..አሁን ብቸኛ ችግሯ ፊቷ ላይ ተሸነታትሮ የሚገኘው ጠባሳ ብቻ ነው….እንግዲህ ግማሽ ፊቷን ባደረሰው በተበታተነው ጠባሳ ውስጥ ምን ያህሉ እንድሚጠፋና ከበፊት ቆዳዋ በቦታው እንደሚመለስ ምን ያህሉ ደግሞ እንዳዛው እንደሚቀር ምንም የምታውቀው ነገር የለም…ያንን ለማወቅ በርከት ያሉ ተጨማሪ የማገገሚያ ቀኖች ያስፈልጋታል…ከዛ በኃላ የቆዳ ስፔሻሊስቶች ጋር ሔዳ ሰርጀሪ መሰራትም የግድ ያስፈልጋት ይሆናል….ለጊዜው ያ እያሳሰባት አይደለም…‹‹እሱን ጊዜው ሲደርስና ሁሉ ነገር ተስተካክሎ ወደቤት ከተመለስኩ በኃላ አስብበታለው››ብላ ወስናለች….አሁን ከጎኗ አቶ ለሜቻ ቁጭ ብለው እያጫወቷት ነው፡፡
‹‹ለልጆቾህ ያለህ ፍቅር ያስገርመኛል››
‹‹አይ ልጄ ሁሉም ወላጆች እኮ ልጆቻቸውን አብዝተው ይወዳሉ…››በትህትና መለሱላት፡፡
‹‹እሱን ማለቴ አይደለም..የእናንተ የተለየ ነው…አይኖችህ ከልጆቾህ ላይ አይነቀሉም….ሙሉ ትኩረትህ ልጆቾህ ላይ ነው..ስለእለት ውሏቸው ታውቃለህ….ጥዋትና ማታ አብረሀቸው ባንድ መሶብ ቀርበህ ሁለቱንም እያጎረስክ ነው የምትበላው፣ብዙ ብዙ ነገር…››
‹‹ልጄ ወድጄ አይደለም እኮ…. እንደምትይው እኔ አባትሽ በብዛት ተትረፍርፎ ያለኝ ፍቅር ነው…ገንዘብ ኖሮኝ ይሄን ስሩ ብዬ መቋቋሚያ..ወይም መነገጃ ጥሪት አልሰጣቸው….ሁል ጊዜ ታዲያ ይሄንን ነገር በምንድነው የማካክሰው ብዬ ሳስብ አንድ የማገኘው መልስ…ጊዜዬንና ፍቅሬን ሳልሰስት መስጠት ነው..አዎ ቢያንስ በዛ ነው ልክሳቸው የምችለው፡››
‹‹ግን እንሱ ምን ያህል እድለኞች መሆናቸውን ያውቃሉ?›› ‹‹አይ እነሱ ሳይሆኑ እኔ ነኝ እድለኛ….ምንም ባላደርግላቸው እንኳን ማንም ፊት በኩራት አባዬ ብለው ይጠሩኛል፡፡በቀደም ለሊሴ ይሄ ፌስቡክ ነው ምን በምትሉት ነገር ላይ በተንዠረገገ ፂሜንና በጎፈረ ፀጉሬ የተነሳሁትን የተጎሳቆለ ፎቶ ለጥፋ አባዬ መልካም

ከመጽሐፍት መንደር💠

25 Jan, 09:22


ባል ካገባች ብዙ ግዜ የሆናት አንዲት ልጅ ባሏ ትንሽ የበጬነት ችግር አለበት እና ምንም ሳይነካት አመታት ስትኖር ቆየችና ሲሰለቻት የሆነ መላ መዘየድ አለብኝ ብላ አስባ አስባ.... ለምን ክፍት ፍት ብዬ ተኝቼ አልጠብቀውም ደንግጦ መሞከሩ አይቀር ብላ ባሏ ጅል ቢጤ ነው ...ከስራ ሲመጣ እንዳለችው ሆና ብልቅጥ ብላ ስጠብቀው ደንግጦ
ባል ፦ " በሬ ነው እንዴ እንዲህ በቀንዱ የቀደደሽ "
ሚስትም ፦ " በሬ አይደለም የቀደደኝ ተፈጥሮ ነው ና ንካዉ ብላ ስታስነካዉ ፍም መስሎ ተነርቶ አብጦ ፍንትዉ ብሎ እሰተ ጎመራ መስሏል “ ወዲያዉ ብድግ አለበት ጎትታ እራሷ አስተካክላ ከታ አቀመሰችው በቃ ጣመው ማታም ቀንም እዛው መጣድ ሆነ ስራው... "እንደው ፈጣሪ ካልጠፋ ቦታ ከፍ አርጎ በበሳው ይል ጀመር" 🤣
ታዲያ አንድ ቀን የልጅቷ አባት በንግድነት መጡ
ባል ደፋ ቀና ብሎ አስተናገዳቸውና እንደው የውዴታው የአክብሮቱን ሚስቱን ጠርቶ
"እረ ከዚያ ከሚጥመው ነገር ሳይቀምሱ እንዳይሄዱ አቅመሻቸው " እያለ አዛ ሲያረጋት ሚስትየው ገልመጥ ብታረገውም አልገባው አለ
በቃ አባት ከፋቸው ብዙም ሳይቆዩ ቤታቸው ተመለሱ
በርላይ ሚስታቸውን ሲያገኙ

" ልጅሽ ከዚያ ነገር አቅምሻቸው እያለ ትከልክለኝ” 🤣🤣🤣🤣

ከመጽሐፍት መንደር💠

23 Jan, 19:23


‹‹የተለየ ስትል?› ‹‹እስከአሁን ወደእኔ መጥተው የሚያናግሩኝ ከሁለት አንዱ ማለቴ ባልዬው ወይም ሚስትዬው ናቸው….የእናንተ ግን ልጃችሁ ነች ያናገረችኝም የቀጠረችኝም፡፡››
‹‹አዎ እሱስ ትክክል ነህ››
‹‹ስለዚህ አሁን ስራችንን ስንጀምር እሷን እያሰብን መሆን አለበት ፡፡በፍቅር የታነፀ ትዳር ውስጥ ያላደጉ ልጆች በመጨረሻ በስነ-ልቦናም ሆነ አካላዊ በሽታ እንደማያጣቸው የተረጋገጠ ነው። ልጅ ስናሳድግ ጥሩ ልብስ ፣ጥሩምግብና ጥራቱን የጠበቀ ትምህርት እንዲያገኙ መጣር ብቻ ሳይሆን የተሞላ ፍቅርም እየመገብን ማሳደግ እንዳለበት እንደወላጅ ግንዛቤው ሊኖረን ይገባል።የመፈቀር እና የመፈለግ ስሜት ማጣት በከፍተኛ ሁኔታ የልጆችን በራስ የመተማመን ችሎታን ከመሸርሸሩም በላይ ለአእምሮ ውጥረትና ድብርትም እንዲዳረጉ ያደርጋቸዋል።ለልጆች በፍቅርና በእንክብካቤ ማደረግ ደስተኛ ሆኖ ለመኖር ብቻ ሳይሆን ጤነኛም ሆኖ ለመኖር በጣም አስፈላጊ ነገር ነው።በወላጆቹ የሚወደድ እና ወላጆቹም የሚወድት ልጆች በጣም ደስተኛ ናቸው።በፍቅር ውስጥ መኖር ጤነኛ ሆኖ ለመኖር እና የበሽታ የመከላከል አቅማችንን ለመጨመር እንደሚያግዝ በሳይንስ የተረጋገጠ ነው።ስለዚህ ልጆቻችን በፍቅር ታንፀው የመፈለግና የመወደድ ስነልቦና ኖሮቸው ማደግ አለባቸው፡፡ለዚህም ወላጆች ሁሉ ትኩረት ሰጥተው መስራት አለባቸው፡፡፡ እንደውም እናንተ እድለኛ ናችሁ፡
‹‹እድለኛ ናችሁ ስትል?››
‹‹እንዴ በፀሎት እኮ በጣም የምትገርም ብስልና በቀላሉ የማትሰበር ልጅ ነች፣አብዛኞቹ በእሷ እድሜ ያሉ ልጆች በእንደዚህ አይነት ችግሮች ውስጥ ሲያልፉ ከፍተኛ ድብርት ውስጥ ይገቡና ለተለያዩ ሱሶች ይጋለጣሉ ..ከዛም አልፈው በህይወት ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ይገቡና እራሳቸውን ወደማጥፋት ይሄዳሉ….በፀሎት ግን ያደረገችው ከውጥረቱ ራሷን ዞር አድርጋ እናንተን ለመርዳትና ወደመስመር ለመመለስ መጣር ላይ ነው ያተኮረችው››
‹‹አዎ እውነትህን ነው …በልጄ ታላቅ ኩራት ተሰምቶኛል….ምንም ጭረት ሳይነካት ወደቤቷ እንድትመለስ ማድረግ ያለብኝን አደርጋለሁ..ማለት ሁለታችንም ማድረግ ያለብንን እናደርጋለን አይደል ስንዱ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…ለዛም አይደል እዚህ የተገኘነው››

‹‹እንግዲያው ጀመርን …ከአሁን በኃላ የምናወራውና የምንናገረው ሁሉ እየተቀዳ ነው.››.ብሎ አይፓዱን አስተካክሎ ተጫነውና ቦታውን ይዞ ተቀመጠ…››
ለሶስት ሰዓት ቀጠለ…..በመጀመሪያ ወ.ሮ ስንዱ አቶ ኃይለመለኮት ላይ ያላቸውን ቅሬታ እስከአሁን በደሉኝ የሚሉትን ነገር እንዲያወሩና አቶ ኃይለመለኮት ደግሞ ለደቂቃ እንኳን ሳያቆርጡ እንዲሰሙ አደረገ…በቀጣዩ ሰዓት ደግሞ አቶ ኃይለልኡል በተራቸው ሚስታቸው ላይ ያላቸውን ቅሬታ በዝርዝር እንዲናገሩ አደረገ……..ቀጣዩን አንድ ሰዓት ደግሞ እራሱ ሰሎሞን ጥያቄ እየጠየቃቸው ሁለቱም ተራ በተራ እዲመልሱ ተደረገና የጥዋቱ ክፍለጊዜ አለቀና ሶስቱም ተያይዘው ወደሳሎን ሄዱ ..ምሳው በስርአት ተዘጋጅቶ ስለጠበቃችው ሶስቱንም ጠረጴዛውን ከበው ፀጥታ በተጫነው ና እርስ በርስ በተፈራራ በሚመስል ሁኔታ ምሳቸው ተበልጦቶ አለቀ..ብና ተፈልቶ ስለነበረ በረንዳ ላይ ቁጭ ብለው ንፋስ እየተቀበሉ ጠጡ
‹‹አሁን ለአንድ ሰዓት ያህል መኝታ ክፍላችሁ ገብታችሁ አረፍ በሉ….ሰዓት ሲደርስ እኔ መጥቼ ቀሰቅሳችኃላው››
እሺ ብለው ሁለቱም ከመቀመጫቸው ተነሱ..ሰለሞን ከኃላ ተከተላቸው….››መኝታ ቤታቸው እንደደረሱ ሊከፍቱ ሲታገሉ‹‹ይቅርታ ሳልነግራችሁ መኝታ ቤታችሁ ተቀይሮል..ተከተሉኝ››ብሎ ቀደማቸው፡፡
‹‹የማ…? የእኔም ነው የተቀየረው?››
‹‹አዎ ወ.ሮ ስንዱ….ሁለታችሁም ተከተሉኝ..››
ግራ በማገባት ሁለቱም በዝምታ ከኃላው ተከተሉት …የኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ካለው በራፍ ሲደርስ ቆመና ከፈተው….‹‹ግቡ ››
‹‹ማ እኔ ነኝ እሷ?››
‹‹ሁለታችሁም››
እርስ በርስ ተያዩ…ቀጥሎ በጋራ እሱ ላይ አፈጠጡበት…አንድ ክፍል ውስጥ አብረው ከተኙ አስር አመት አልፏቸዋል..አሁን በአንዴ እንዴት….?ጉዳዩ ሁለቱንም እኩል ነው ያስበረጋጋቸው፡፡

ጫን ባለ የአዛዥነት ቃና‹‹እባካችሁ ግቡ››አላቸው
ምርጫ ስላልነበራቸው አቶ ኃይለልኡል ቀድመው ገቡ…ወ.ሮ ስንዱ ተከተሏቸው….ሁለቱም ጎን ለጎን ቆመው ክፍሉን ዙሪያ ጋባ ቃኙት …ሻንጣቸው ሆነ ጠቅላላ እቃቸው በየቦታው ተቀምጦል…ሁለት አልጋ ማዶ ለማዶ ግድግዳ ተጠግቶ ይታያል…፡፡
ያው ..ሁለት አልጋ አለ …ተነጋገሩና አንዳንደ አንድ ተካፈሉ …በቃ መልካም እረፍት..ሰዓቱ ሲደርስ መጥቼ ቀሰቅሳችኃላው››አለና ከክፍሉ ወጥቶ በራፉን መልሶ ዘግቶላቸው ወደገዛ ክፍሉ ሄደ፡፡
///
የሁለት ሰዓት የረፍት ጊዜ ከሰጣቸው በኃላ በጥዋቱ ጊዜ ባለው ፕሮግራም የቀረጸውን ወደኮምፒተሩ ገለበጠና ይዞ ወደእነሱ ክፍል አመራ…በስሱ ቆረቆረ…ወዲያውን ነበር የተከፈተለት፡፡
‹‹መጣህ ..?እየጠበቅንህ ነበር››
‹‹አዎ መጥቻለው››
‹‹ስንዱ ተነሽ..እንሂድ››አቶ ኃይለልኡል ተናገሩ፡፡
‹‹አይ ቆይ መሄድ አያስፈልግም ….እዚሁ እናድረግው››
‹‹ይሻላል ..እሺ ግባ..››ብለው በራፉን ለቀቁለትና ወደውስጥ በመመለስ አልጋቸው ጠርዝ ላይ ተቀመጡ ፡፡ወ.ሮ ስንዱም የራሳቸው አልጋ ላይ እንደተቀመጡ ነው፡፡
ወንበር ሳባና ከሁለቱ መካከል ተቀመጠና ኮምፒተሩን ጠረጳዛ ላይ አስቀመጠው፡፡
‹‹ይሄውላችሁ በትዳር ውስጥ ችግር መፈጠርና አለመስማማት የእናንተ ብቻ ሳይሆን የሚሊዬን ጥንዶች ችግር ነው..እመኑኝ ያልተስማማንበት ነገር ይህ ነው ያ ነው ብላችሁ ቀኑን ሙሉ ስትዘረዘሩ ብትውሉ የእናንተ ከሌላው ትዳር ውስጥ ከተፈጠረው ችግር የተለየ ሊሆን ይችላል እንጂ የባሰ ግን አይደለም፡፡ስሙኝ አብዛኛውን ጊዜ በትዳር ውስጥ ችግር ሲከሰት በትዳር ውስጥ ችግር የፈጠረውን ነገር ከማየት ይልቅ እራሱ ትዳርን እንደችግር የመውሰድ  አዝማሚያ  ይታያል።ያ  ደግሞ  ከትዳራቸው  ውስጥ  ሾልኮ  ስለመውጣት

ስለመፋታት እንዲያስብ ያደርጋቸዋል።እንደሀሳባቸው ትዳራቸውን ፈተው የተሻለ ወዳሉት ወደሌላ ትዳር መሸጋገር ቢችሉም ችግሩም አብሯቸው ነው ወደአዲሱ ትዳራቸው የሚሸጋገረው።
መፍትሄው ትዳሩን እንደችግር ወስዶ ያልሆነ ድምዳሜ ላይ ከመድረስ ይልቅ ትዳሩ ውስጥ የተከሰቱ ችግሮች ምን ምን ናቸው ብለው በመለየት እነሱን ለማስወገድ መጣር እና በዛ ሂደት የጋብቻውን ህልውና ማስቀጠል ይበጃል።ምክንያቱም የመኪናህ ጓማ ቢያልቅ ጎማውን ትቀይራለህ እንጂ መኪናዋን ሙሉ በሙሉ አታስወግድም።አይደለም ጎማ ሞተሩ ቢነክስ እንኳን ሞተር አስወርደህ ከእንደገና ተፈቶና ተበታትኖ ችግሩ ተለይቶ ከተወገደ በኃላ መልሶ ይገጣጠምና መኪናው እንደነበረ ይቀጥላል... ጋብቻም እንደዛ ነው የሚደረገው።እና አሁን እያደረግን ያለነው በመሀከላችሁ ያለውን ችግር የመቃቃራችሁን መንሴ መለየት ነው፡፡አሁን በጥዋቱ ክፍለ ጊዜ ሁለታችሁም የተናገራችሁትን እዚህ ኮምፒተር ላይ ከፍትላችኃላው በጋራ አብራችሁ ታዩታላችሁ…ይሄ መልሳችሁ የተናገራችሁትን እንድታዳምጡና የትኛው ትክክል ነው..የትኛው ንግግራችሁ ተጋኗል የሚለውን መልሳችሁ እንድታስበቡበት ይረዳችኃላ…

ከመጽሐፍት መንደር💠

23 Jan, 19:23


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራ ሰባት

ይዘውት የሄዱት ቦታ ከቢሾፍቱ ከተማ በባቦጋያ ሀይቅ አካባቢ ከከተማው ወጣ ብሎ የሚገኝ ቪላ ነው፡፡ይህ ቪላ ቤተሰቡ ከውጥረት ረገብ ለማለት ሲፈልግ የሚገለገልበት ስፋራ ነው፡፡ለአለፉት አንድ አመት ከግማሽ ማንም ዝር ብሎበት አያውቅም ነበር፡፡ሰለሞን ስፍራውን ሲያይ ከውበትም ሆነ ከፀጥታ አንፃር ሲታይ ሙሉ በሙሉ እሱ እንደሚፈልገው አይነት ሆኖ ነው ያገኘው፡፡አንድ ሺ ካሬ ሜትር በላይ የሚሆን ቅፅር ግቢ ነው፡፡መሀከል ላይ ግዙፍና ባለግርማ ሞገስ ጥንታዊ ግን ደግሞ ጥሩ ይዞታ ላይ ያለ ግዙፍ ቪላ ቤት አለበት…ግቢው ውስጥ እድሜ ጠገብ ግዙፍ ባለግርማ ሞገስ የባህር ዛፍና የጥድ ዛፎች ስብስባ ላይ እንደተቀመጠ ታዳሚ እዚህም አዛም ዙሪያውን ተሰራጭተው ይታያሉ…ገና ግቢውስጥ ገብተው እንዳቆሙ የቤት ጠባቂዎች በልና ሚስቶች በፍጥነት መጥታው መኪናዋ አጠገቡ ቆሙ፡፡መኪናዋን ሲነዳ የነበረው እራሱ ሰሎሞን ስለነበረ….ሞተሩን

አጠፋና ቀድሞ ወረደ…አቶ ኃይለመለኮትን ወ.ሮ ስንዱም ወረዱና ከጠባቂዎቹ ጋር ሰላምታ መለዋወጥ ጀመሩ…ከዛ ቀጥታ ወደ ቤት ነው የገቡት….ቀድመው ደውለው ስለነበር..እቤቱ ምሉ በሙሉ ፀድቶና የእነሱም መኝታ ክፍል ተዘጋጅቶ ነበር የጠበቃቸው….
ታፈሰ ‹‹ጋሼ ባዘዙኝ መሰረት ሶስት ክፍል ለመኝታ አዘጋጅቼያለው…ይሄው እርሶ እዚህ ግቡ….እትዬ ደግሞ ቀጥሎ ያለው …ወንድም አንተ ደግሞ የፊት ለፊተኛው ክፍል…..ድንገት ስለሆነብን ሁሉንም ነገር ማዘጋጀት አልቻልንም….የጎደለውን ንገሩኝና ከተማ ወጣ ብዬ ገዝቼ አሟላላሁ››
አቶ ሃይለመለኮት ወደሰለሞን እያመለከቱ‹‹ተፈሰ…ይሄውልህ እዚህ 15 ቀን ነው የምንቆየው….በዚህ 15 ቀናት ውስጥ የእኛም ሆነ የአንተ ሀለቃ እሱ ነው….ምንም ነገር ቢያዝህ እሱ ያለውን ነው የምታደርገው…እኛም እንደዛው››ሲሉ መመሪያ አስተላለፉ፡፡
ታፈሰ…የአቶ ኃይለልዕልን ንግግር ከበፊት ቆፍጣና ባህሪያቸው ጋር አልሄድ ስላለው ..ግራ በመጋባት አፍጥጦ ያያቸው ጀመር…እሱ እንደሚየውቀው እኚ ግዙፍ አዛውንት ለሰው ምንም ሊሰጡ ይችላሉ የአዛዥነት ቦታቸውን ግን ፈፅሞ ሸርፈው እንኳን ለሌላ ሰው ይሰጣሉ ብሎ ማመን ይከብደዋል፡፡
‹‹ታፈሰ ..ሰምተኸኛል…የሁሉ ነገር አዛዣችን እሱ ነው››ደገሙለት፡፡
‹‹አዎ ..ገባኝ ጌታዬ…እንዳሉት ይደረጋል››
‹‹አሁን ሁላችንም ወደክፍላችን እንግባና ትንሽ አረፍ እንበል ..አይደል?››ወ.ሮ ስንዱ የሰለሞንን አይኖች በልምምጥ እያዩ ጠየቁ፡፡
ቆይ አንዴ ክፍላችሁን ልይ ብሎ..ለአቶ ኃይለልኡል የተመደበውን ከፍቶ አየው፡፡ቀጥሎ የወ.ሮ ስዱን ከፈተና አየው፡፡‹‹ጥሩ በቃ ግቡና እረፉ››
ሁለቱም ገቡና የየራሳቸውን ክፍል ዘጉ
‹‹አንተም ወደክፍልህ ግባ ጌታዬ..እኔ ደግሞ እቃችሁን ከመኪና ላውርድ››
‹‹ቆይ አብሬህ ልምጣ››ብሎ ተከተለው፡፡የታፈሰ ባለቤት ለእንግዶቹ ምግብ እያበሰለች ስለነበር ታፈሰ እቃዎቹን ማለት ይዘው የመጡትን አስቤዛ እና ሻንጣዎች ሲያወርድና ወደቤት ሲያስገባ ሰሎሞን አገዘው፡፡እንደጨረሱ፡፡‹‹ተለቅ ያለ ክፍል የለም?››ሲል ጠየቀው፡፡

‹‹ምን አይነት ክፍል…ማለቴ ለምን የሚሆን?››
‹‹ለመኝታ ቤት የሚሆን ..ሁለት አልጋ የሚያዘረጋ››
‹‹ቆይ ..ኮሪደሩ መጨረሻ ላይ ያለው ክፍል ሰፋ ይላል››
‹‹ማየት እችላለሁ?››
‹‹አዎ ይቻላል….››ብሎ ይዞት ሄደና ከፈተለት…ሰለሞን ወደውስጥ ዘልቆ ሳይገባ በራፉ ላይ በመቆም አንገቱን ወደውስጥ አስግጎ ተመለከተው….አቦራ የጠጣና ለብዙ ጊዜ ጥቅም ላይ ያልዋለ ቢሆንም የሚፈልገው አይነት ክፍል ነው፡፡››
‹‹ታፈሰ ይሄንን ክፍል በአስቸኳይ ልታስፀዳልኝ ትችላለህ….?››
‹‹እችላለሁ..አፀዳዋለው››
‹‹አይ ብቻህን ይከብድሀል..ሰው ቅጠርና በፍጥነት ወለሉም ግድግዳውም ይፅዳ….ውስጥ ያሉት እቃዎችም ወደሌላ ክፍል ይዘዋወሩ››
‹‹እሺ››
ተሰናብቶት ንፁህ አየር ሊቀበልና እግረመመንገዱን አካባቢውን ለመቃኘት ወጥቶ ሄደ፡፡
///
በማግስቱ ጥዋት 3 ሰዓት ላይ ሁለቱንም የማይጣጣሙ ባለትዳሮችን አንድ ክፍል ጎን ለጎን እንዲቀመጡ አደረገና እሱ ከፊት ለፊታቸው ተቀመጠ..ጉሮሮውን አፀዳዳና የመግቢያ ንግግሩን ጀመረ
‹‹በሰዎች መካከል ለተለያየ አለማ ተብለው የሚደረጉ የእርስ በርስ ጉድኝቶችና ቁርኝቶች አሉ፡፡ከነዛ መካከል ግን በጣም ውስብስቡ የጠበቀውና የጠለቀው ግንኙነት በአንድ ወንድ እና ሴት መካከል የሚፈጠር የጋብቻ ጉድኝት ነው፡፡በጋብቻ ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ሁሉ ጊዜ ቀላል የተባለ መንገድ አይገኝም….አንዱ ጋብቻ ውስጥ የሚፈጠረው ችግር ከሌላው ጋብቻ ችግር በአይነትም በይዘትም ፍፁም የተለየ በመሆን ችግሩን ለማስተካከል የሚወሰደውም እርምጃ የዛኑ ያህል የተለያ ነው፡፡በዛ ላይ ሁሉም ችግሮች እዲፈቱ  በጥንዶቹ  መካከል  ስክነት፣  ትዕግስትን፣ጥረትን  እና   እራስ  መግዛትን

ይጠይቃል፡፡አሁን ልብ በሉ ፣ጥረታችን በመካለላችሁ ያላውን ግጭትና ጭቅጭቅ ሙሉ በሙሉ ማስወገድ አይደልም..አይ እንደዛማ አይሆንም እናንተ ሰው ናቸው፣ሁለት ሰዎች ደግሞ በአንድ ጣሪያ ስር አብረው እስከኖሩ ድረስ በሆነ ነገር መነጋገራቸውና በነገሩ ላይ የተለያየ ተቃራኒ ሃሳብ ማንፀባረቃቸው አይቀርም…ስለዚህ መነጋገርና መጨቃጨቃችሁ ኖርማል ነው…አሁን ምንድነው ምናደርገው በማንኛውም ጉዳይ ላይ አለመግባባት ተከስቶ ስትነጋገሩ በምን መልኩ ነው ኮምንኬት የምታደርጉት..?ነገሩን ማስረዳትና ማሳመን ላይ ነው ትኩረታችሁ ወይስ ያንን ምክንያት አድርጎ በስድብና በዘለፋ ማጥቃትና ልብ መስበር…አያችሁ ትልቁ ችግር መጋጨታችን ሳይሆን በያንዳንዱ ግጭታችን አንዳችን ለሌላቸውን የልብ ቁስለትና የነፍስ ህመም መስጠታችን ነው፡፡ማጥፋት ያለብን እርስ በርስ መወጋጋቱን ነው…አንዳችን ሌላችን ላይ በምንም አይነት ሰበብ የሚያቆስል ጦር አስበን አይደለም አምልጦን እንኳን መወርወር የለብንም፡፡
እርስ በርስ ከፍ ባለ ቃላት በተነጋገራችሁ ቁጥር ደግሞ እየተጣላችሁ መሆኑን አታስቡት..መጣላት ቃሉ እራሱ አሉታዊ ነው፡፡እየተጣላችሁ ሳይሆን በጋለ ስሜት እየተነጋገራችሁ ነው፡፡በቃ እንዲህ ነው ማሰብ ያለባችሁ፡፡እንደዛ ካሰባችሁ ቀጥታ ችግሩ በጋለ ስሜት መነጋገራች ብቻ ስለሆነ ስሜታችሁን በማረጋጋት ነገሩን ትፈታላችሁ፡፡እየተጣላን ነው ብላችሁ ካሰባችሁ ግን ገና ይቅርታ የሚጠይቅ ሰው ወይም ሽማግሌ ልትፈልጉ ነው፡፡ልብ በሉ ጮክ ብሎ መናጋገር ሁል ጊዜ መጣላት አይደለም ..አዎ አብዛኛውን ጊዜ በጋለ ስሜት መነጋገር ነው፡፡ሌላው በምንም አይነት ሁኔታ ንግግራችሁ ሰው ፊት አይሁን፡፡የምንወደው ሰው ላይ ያለንን ቅሬታ ብቻውን በሆነበት ጊዜ ነው መናገር ያለብን…እንደዛ ሲሆን ነው ውጤታማና ጥፈቱን ለማረም ፍቃደኛ የሚሆነው…ወቀሳው..ሰው ፊት ሲሆን ግን ሰውዬው የበለጠ በእኛ ቅሬታ እንዲያድርበት መንገድ ያመቻቻል፡፡
‹‹እንግዲ ሁላተችሁም እንደምታውቁት አሁን ለእኛ እዚህ መገኘት ዋናዋ ምክንያት በፀሎት ነች፡፡እኔ በስራ በተለይ ከሀገር ውጭ በነበርኩበት ጊዜ በጣም ብዙ ባለትዳሮችን አማክሬያለሁ ትዳራችውም መካከል ያለውን ችግር በመተጋገዝ ለመፍታት ችያለሁ....በብዙዎችም ረክቼለው..ከብዙ ቤተሰቦች ጋርም እቤተሰብ ለመሆን ችያለው….ግን እመኑኝ እንዲህ እንደእናነተ የተለየ ጉዳይ ገጥሞኝ አያውቅም››

ከመጽሐፍት መንደር💠

23 Jan, 17:37


ስርዝ ድልዝ ደብዳቤ
(

እዚህ ደብዳቤ ላይ....
ልነግርሽ ያሰብኩት
አስቤ የፃፍኩት
ፅፌ የሰረዝኩት
ሰርዤ የላኩት
ስርዝ ድልዝ ሆኖ አልነበብ ካለሽ
ሳልሰርዘው በፊት …
ሀሳቡ መልእክቱ - ምን ይላል መሰለሽ
.
.
.
.

መግቢያው
መደምደሚያው - ሀተታው በሙላ
ሌላ አይናገርም….
ከናፈቅሽኝ እና - ካፈቀርኩሽ ሌላ፡፡


በላይ በቀለ ወያ

ከመጽሐፍት መንደር💠

22 Jan, 19:26


ሰላም ሰላም ዉድ አንባቢያን እንዴት ናችሁ ሰዉ ሲጠፋ አጠይቁማ😔 
ለማንኛዉም 😁ይቺን ጥያቄ ካነበብኩት ላካፍላችሁ እስቲ ተሳተፉ👇👇👏👏👏
አባባሉን ጨርሱት 
1. የግዜ እንጂ የሰው....... 
2. የሚያልፍ ቀን.......
3. እንዲህ ልጠግብ....
4. መሸጥ የለመደ..  
5. ሁሉን ቢናገሩት.....

ከመጽሐፍት መንደር💠

22 Jan, 18:51


.ከሶስት ቀን በኃላ
አቶ ለሜቻ ነገሮችን ተቀብለው….ቱታቸውን ለብሰውና ሌሎች ሁለት ሰዎችን ቀጥረው ቀጥታ ቤቱን ወደመገንባት ስራ ገቡ..ይሔ ሁኔታ የቤቱን ሰው ሁሉ በጣም ሲያስደስት በፀሎትን ደግሞ በይበልጥ አስፈነጠዛት፡፡ቢያንስ አንድ ነገር ልታደርግላቸው በመቻሏ የውስጥ እርካታ ተሰማት….ማንነቷን በሚያቁበት ቀን መልሰው ብስጭት እና ቁጭት ውስጥ እንደሚገቡ እርግጠኛ ነች..ቢሆንም ግን ምርጫ ያላትም…በዚህ ጉዳይ ላይ እሷቸው ትክክል ናቸው ብላ አታስብም…ሰው እርስ  በርሱ  መረዳዳትና  አንዱ  የሌላውን  ኑሮ  ማቃናት  ያለና  የነበረ  ተግባር

ነው….እሷቸው ይሄንን ጉዳይ ከክብር አንፃር ማየታቸው የእሷቸውን ኑሮ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላ የቤተሰቡ ኑሮ እየጎዳ ያለው፡፡
ስራውን ከጀመሩት በኃላ እንደፊቱ አልከበዳቸውም..እንደውም ይበልጥ ጉጉት አሳደረባቸውና ከወር በኃላ ለሚከበረው ከልጃቸው የ3ተኛ አመት የሙት አመት መታሰቢያ ቀን በፊት ጥንቅቅ አድርገው መጨረስ አቅደው ቀን ከሌት መስራት ጀምረዋል፡፡አዎ ልጃቸው በህይወት ብትኖር ኖሮ እሰከዛሬ ይሄንን ቤት ሰርታ እንደምትጨርስ ያምኑ ነበር…አሁንም የሙት አመት መታሰቢያዋን ሲደግሱ የሙት መንፈሷ ሊያያቸው እንደሚመጣ እርግጠኛ ናቸው… ታዲያ ያንን ጊዜ ለእነሱ ቤት መስራት ህልሞ ስለነበረ ተሰርቶ ስታየው በጣም ደስ ብሏት እንደምትመለስ እርግጠኛ ናቸው…፡፡
እንደ ወትሮ መሽቶ ቤተሰቡ ሁሉ ተሰብስበው በሳቅና በጫወታ እራታቸውን በልተው ቡና ተፈልቶ ተጠጥቶ ከተጠናቀቀ በኃላ አምስት ሰዓት አካባቢ ሁሉም ሰው ወደመኝታው ሄደ…ፊራኦልም የውስጡን በውስጡ ይዞ ልክ እንደወትሮ እንደተኛ ሰው ሆኖ አደፈጠ…..በጨለማ ውስጥ አፍጥጦ እስከሰባት ሰዓት ድረስ በሀሳብ ሲባትት ነበር…ልክ ሰባት ሰዓት ሲሆን ቀስ ብሎ ከተኛበት ሶፋ ላይ ተነሳና መብራቱን አበራ ..የቤቱን ዙሪያ ገባ ቃኘ….በፀሎትና ለሊሴ ተዘረጋግተው እንደተኙ ነው፡፡ከወላጆቹ ክፍልም ምንም የሚሰማ እንቅስቃሴ የለም…..ቀስ ብሎ ወደሴቶቹ መኝታ ተጠጋ… ሁለቱም አይናቸውን ጨፍነው ጥልቅ የሚባል እንቅልፍ ውስጥ ናቸው፡፡ይሄኔ ህልም እያለሙ እንደሚሆን ገመተ…ቀስ አለና በፀሎት በተኛችበት በኩል ዞሮ ከራስጌዋ ጎን ካለ መቀመጫ ላይ ተቀመጠ…ቁልቁል አዘቅቆ አያት…ቀስ ብሎ እጁን ዘረጋና ፊቷ ላይ የተጠቀለለውን ሻርፕ ጫፍ ይዞ ጎተተው…ቀስ በቀስ ከፊል ፊቷ እየታየው መጣ …ሻርፑን ሙሉ በሙሉ ከፊቷ አስወገደእና በትኩረት ይመለከታት ጀመር…..ድንገት ተገላበጠችን በጀርባዋ ተንጋለለች ..በዛን ጊዜ ሙሉ በሙሉ ለእይታው ተጋለጠች….አሁን እርግጠኛ ሆነ…ምንም እንኳን የተወሰነ መጓሳቆል ቢታይባትም …ምንም እንኳን ቀኝ የፊቷ ክፈል ላይ ብዛት ያላቸው ጭረቶችና ጠባሳዎች ቢኖሩም እራሷ ነች…ለአመታት በድብቅ ከሩቅ ሲያያት የነበረችው..የእህቱን ውድ ልብ በውስጧ የተሸከመችው ልጅ….
‹‹እሺ አሁን ምንድነው የማደርው?››እራሱን ጠየቀ…ቀስ ብሎ ሻርፑን መልሶ ፊቷን ሸፈነና ከተቀመጠበት ተነስቶ መብራቱን አጠፋና ወደ መኝታው ተመለሰ….ሙሉ ለሊቱን እንቅልፍ ሊወስደው አልቻለም…..
አሁን ያወቀውን ነገር ባያውቅ ምኞቱ ነበር….አንዳንድ ማወቆች ሸክማቸው ያጎብጣል..አውቆ የሆነ ነገር ማድረግም አለማድረግም እዲህ አስቸጋሪ ሲሆን ምነው ምንም ነገር ባላወቅኩ ኖሮ ያስብላል፡፡ይህቺን ልጅ አፍቅሯት ነበር…የሞች እህቱን ልብ የተሸከመችው ልጅ መሆኗን ሳያውቅ በፊት ከእሷ ፍቅር ይዞት ነበር..ለእሷም ሆነ ለማንም ይሄንን ስሜቱን ተናግሮ አያውቅም….ግን እሱ በፍቅር እንደተነደፈ እርግጠኛ ነበር‹‹እሺ አሁን ምንድነው የማደርገው….?››እራሱን ጠየቀ…ብዙ ጊዜ ስለፍቅር ና ውበት ሲያወራ እርዕስ የምትቀይረውና ወሬውን የምትገፋው ለምን እንደሆነ አሁን ገባው…‹‹ይህቺ ልጅ ተአምረኛ ነች››ሲል አሰበ‹‹እራሷን በበሬዱ ቦታ ለመተካት እየጣረች ነው…አዎ ወደቤታችን የመጣችው ድንገት በአጋጣሚ ሳይሆን ሆነ ብላ አስባና አቅዳበት ነው… አንተ ወንድሜ ነህ ስትለኝ እንዲሁ ለአባባል ብቻ የምትጠቀምበት ይመስለኝ ነበር..ለካ እሷ ከአንጀቷ ነው፡፡››ሲል አሰበና በድቅድቅ ጨለማው ፈገግ አለ….‹‹ይሄን ጉድ ወላጆቹ ሲሰሙ ምን አይነት ምላሽ እንደሚሰጡ አሰበ…..ለመገመት አንኳን አልቻለም፡፡በተለይ አባቱ በበሬድ ጉዳይ ስሜተ ስስ እንደሆነ ያውቃል….ፈራ …በጣም ፈራ…. ‹‹ግን እሷስ እስለመቼ እንዲህ ከወላጆቾም ተሰውራ እውነቱን ከእኛም ደብቃ ትዘልቃዋለች..?እቅዷ ምንድነው?››ሊገባው አልቻለም፡

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇
ከመጽሐፍት መንደር
ከመጽሐፍት
መንደር
♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ከመጽሐፍት መንደር💠

22 Jan, 18:50


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራስድስት

በፀሎት ግቢው ውስጥ ባለ የዛፍ ጥላ ስር ወንበር አውጥታ ቁጭ ብላለች…ፊራኦል ግንዱን ተደግፎ እሷን በትኩረት እያያት እያወሩ ነው፡፡ ወሬው ስለሟች እህቱ ስለበሬድ ነው፡፡በእሷ ሞት ምክንያት ምን ያህል እንደተጎዳና የእሱ ብቻ ሳይሆን የቤተሱም ኑሮ እንደተመሰቃቀለ እየነገራት ነው፡፡
‹‹ሀዘንንም ጨመሮ ሁሉም ነገር ጊዜያዊ መሆኑን አውቀህ ከክስተቶች ጋር እራስን አታጣብቅ…ከነገሮች ጋር እራስህን አስማምተህ ፍሰስ..እናም እራስህን ደስተኛ ለማድረግ ሞክር..ጊዜ የማይፈውሰው ህመም የለም››ብላ ልታፅናናው ሞከረች፡፡

‹‹ጊዜ ሁሉንም ህመሞች እኩል አይፈውስም….አንዳንድ ህመሞች በዕድሜያችን ልክ ተሰፍረው የተሰጡን ናቸው..አንዳንድ ስብራቷች የዘላለም ናቸው፡፡እህቴ ከሞተች ሁለት አመቷ አልፎ ሶስተኛውን ልናገባድድ ነው…ግን አሁንም ድረስ አባዬ እህህ እንዳለ ነው….እማዬን እደምታያት አይኗን እንዲህ የደከመው ከእድሜ የመጣ ህመም ወይም ጭስ አይደለም…የዘወትር ለቅሶ ነው….አየሽ አንዳንድ ስንጥቆች እንዲህ በቀላሉ ጊዜ ስላለፈ ብቻ አይደፈኑም…››
‹‹ትክክል ልትሆን ትችላለህ …ግን መሞከሩ አይከፋም…››
‹‹.በይ አሁን ወጣ ብዬ ልምጣ፡፡››
‹‹ሩቅ ካልሆነ ለምን እኔንም ይዘኸኝ አትወጣም?››
‹‹አይ ይሄንን ሻርፕሽን ከላይሽ ላይ ካልጣልሽ ከእኔ ጋር ከእዚህ ጊቢ መውጣት አትችይም..ጓደኞቼ እኮ ያቺ ሊንጃ ዘመድህ እያሉ ፉገራቸውን አልቻልኩትም››
‹‹እንዲሁ …ከአንቺ ጋር መታየቱ ይደብረኛል አትልም››
‹‹አይ… ያ እውነት እንዳልሆነ አንቺም ታውቂያለሽ…ለማንኛውም ቀላል ነገር ነው የጠየቅኩሽ…ሻርፕሽን ከላይሽ ላይ አንሺና አብረን እንሂድ››
‹‹አንተ ባለጣባሳዋ ዘመድህ ከሚሉህ ሊንጃዋ ቢሉህ አይሻልህም?፡፡››
‹‹አይ ግድ የለም..ባለ ጠባሳዋ ቢሉኝ ይሸለኛል…››
‹‹እንግዲያው ቀረብህ ሂድ በቃ››
‹‹አንቺም ቀረብሽ…ቸው››ብሏት ወጣ……ፊራኦል ሆነ ብሎ በአላማ ነው እንደዚህ የሚያደርጋት፡፡በፀሎትን መጠራጠር ከጀመረ ቀናቶች አልፈዋል…የምትለውን አይነት ልጅ እንዳልሆነች ውስጡ እየነገረው ነው….ምን አልባት የተጠራጠረው እውነት ከሆ ምን እንደሚያደረግ ግራ ገብቷታል….አጋልጦና አሳልፎ ይሰጣታል? ለአባቱ ይናገራል…?ለወላጆቾ አሳውቆ ለሽልት ያቀረብትን 5 ሚሊዬን ይቀበላል…?እንደዛ ካደረገ በእርግጠኝነት አባቱን ለዘላለም እንደሚያጣ እርግጠኛ ነው…ማጣት ምን እንደሆነ ደግሞ በእህቱ ሞት በደንብ ስለተማረ አባቱን ደግሞ ካጣ ከዛ በኃላ ሰው እንደማይሆን እርግጠኛ ነው…ብቻ የተወሳሰብ ነገር ውስጥ እንደገባ እርግጠኛ ነው….አንዳንዴ ነገሮችን በጥልቀት ከመቆፈር እራሱን ማገድ

ቢችል ይመኛል…ምንም ትሁን ማንም ችላ ብሎ ሊተዋት ይወስንና ውሳኔውን ለረጅም ጊዜ አፅንቶ ማቆየት አይችልም….‹‹ውይ በፀሎት….ምን አይነት ልጅ ነሽ?››እንደጀማሪ እብድ ብቻውን መንገድ ላይ እየለፈለፈ እየሄደ ነው፡፡
ከሄደ በሃላ ግን እሷ ከፍተኛ ትካዜ ውስጥ ነው የገባችው፡፡ይሄ ልጅ ሙሉ ፊቷን እንድታሳየው ወጥሮ ይዞታል…አውጥተው አይናገሩ እንጂ የቤቱ ሰው ሁሉ ቀንና ለሊታ ፊቷን ጠቅላላ አልብሶ በአንገቷ ዙሪያ ተጠፍሮ ታስሮ የሚውለውን ሻርፖን ከዛሬ ነገ ለምን አይነሳም? የሚሉ ጥያቄ በውስጣቸው እየተጉላላ እንዳለ እርግጠኛ ነች….ይሄንን ማድረግ አትችልም…ቀኑ ከመድረሱ በፊት እራሷን ማጋለጥና ማንናቷን ማሳወቅ ሁሉን ነገር ነው ትርምስምስ የሚያደርግባት፡፡ከመቀመጫዋ ተነሳችና ከሻንጣዋ ውስጥ ስልኳን በማውጣት ወደጓሮ ሄደች …ወደእሷ ሰው ከመጣ በግልጽ ለማየት የሚቻላትን ቦታ መርጣ ተቀመጠችና የጠፋውን ስልክ አበራችው…..ሰሎሞን ጋር ደወለች፡፡
‹‹እሺ እንዴት ነህ?››
‹‹ሰላም ነኝ..አንቺ ደህና ነሽ….ከአሁን አሁን በደወለች እያልኩ በማስብበት ጊዜ ነው የደወለሽው››
‹‹ምነው አዲስ ነገር አለ?››
‹‹አዎ …ዛሬ አባትሽ ቤት አስጠርተውኝ ነበር››
‹‹አትለኝም!! ታዲያ እንዴት ሆነልህ?››
‹‹ሁሉ ነገር አንቺ እዳልሽው ነው የሆነው…ስለእኔ በድንብ ሲያጠኑ ነበር የከረሙት..የስልክ ልውውጣችንንም አግኝተው አዳምጠውታል…..በአጠቃላይ እውነቱን እንደተናገርኩ ተረድተዋል››
‹‹እና መጠጨረሻው ምን ሆነ?››በጉጉት ጠየቀች
‹‹ምን ይሆናል..?ያው አሁን ቁጭ ብዬ ዝርዝር እቅድ እያወጣሁ ነው….ሁለቱም ነገሮችን መስመር ለማስዝ ያልኳቸውን እንደሚያደርጉ ውሳኔያቸውን አሳውቀውኛል፡፡››
‹‹በጣም ደስ ይላል….በዚህ ፍጥነት ይስማማሉ ብዬ አላሰብኩም ነበር››

‹‹እኔም ከአንቺ በላይ ፈርቼ ነበር…ግን አንቺን በጣም ስለሚወዱሽ ምንም ምርጫ የላቸውም…እንደተረዳሁት ከሆነ ሁለቱም ጋብቻቸውን ስለማዳንና ፍቅራቸውን ስለማደስ ደንታም የላቸውም…ግን ደግሞ በምንም ብለው በምንም አንቺን መልሰው እጃቸው ለማሰገባት ከልብ ይፈልጋሉ..ለዛ ነው በፍጥነት የተስማሙት፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነህ…እሷን ለማግኘት እርስ በርስ ተገዳደሉ ብተላቸው በተሻለ ቀሏቸው አሁን ከፈጠኑት በላይ ፈጥነው ያደርጉት ነበር፡፡››
‹‹እንዴ ..አንቺ ደግሞ አጋነንሺው…እርስ በርስ ከተገዳደሉ እንዴት ብለው ነው አንቺን የሚያገኙሽ…ለማንኛውም ስራው ስለተጀመረ ስልክሽን ባትዘጊው ጥሩ ነው…ምክንያቱም ስለእነሱ አነሱን ጠይቄ ማወቅ የማልችለውን መረጃ አንቺ ነሽ ልትነግሪኝ የምትችይው…ለዛ ደግሞ የግድ በፈለኩሽ ግዜ ማግኘት አለብኝ፡፡››
‹‹በስልኬ ተከታትለው ከደረሱብኝስ?››
‹‹ስልኩን አዲስ ቁጥር ነው…ማንም አያውቀውም ያልሺኝ መስሎኝ?››
‹‹አዎ ትክክል ነህ አዲስ ነው…አሁን ግን አንተ ታውቀዋለህ››
‹‹እኔ ለእነሱም ሆነ ለሌላ ለማንም ሰው አልሰጥም…ለአንቺ ስል ሳይሆን ለራሴ ስል….ሁለተኛ አሁን አንቺን መፈለጉን እርግፍ አድርገው ትተው ጋብቻቸውን ላይ ሙሉ ትኩረት እንዲያደርጉ አጥብቄ ነግሬያቸዋለሁ እነሱም ሙሉ በሙሉ ተስማምተዋል››
‹‹እና መቼ ልትጀምሩ ነው?፡፡››
‹‹እንደነገርሺኝ በፍጥነት ወደቤትሽ መመለስ ትፈልጊያለሽ..ስለዚህ ምንም ጊዜ ማባከን አያስፈልግም…ነገ ስራ እንጀምራለን…ለሚቀጥሉት 15 ቀን ቢሾፍቱ ወዳለው ቤታችሁ እንሄዳለን ፡፡ከዛ በኃላ ደግሞ ውጤቱን እናይና ወደአንዱ ጋር እንሄዳለን፡፡;;
‹‹እንዴ ሁለቱም ለመሄድ ተስማሙ››
‹‹አዎ…በደንብ ተስማምተዋል..ነገ ሶስት ሰዓት አዲስአበባን ለቀን እንወጣለን››
‹‹ይገርማል….በዚህ ፍጥነት ከከተማው ይዘኸቸው ትወጣለህ ብዬ አላሰብኩም ነበር››

‹‹አየሽ ነገሩ ለአመታት የተከማቸና ስር የሰደደ ስለሆነ …..ሙሉ ትኩረት ይፈልጋል….አዲስአባባ ተቀምጦ ደግሞ በሙሉ ትኩረት እንዲህ አይነት ነገር ለመከወን ምቹ አይደለም….ለዛ ነው ከከተማው ላርቃቸው የፈለኩት››
‹‹በጣም እያስደስትከኝ ነው…››
‹‹ተይ እንጂ….ገና ምኑም ሳይያዝ ምስጋና ከጀመርሽ በኃላ ጥሩ አይመጣም››
‹‹አያያዝህን አየሁት …እንደምታሳከው በጣም ነው ምተማመንብህ››
‹‹አመሰግናለሁ›››
‹‹እሺ.. በቃ ቸው››
‹‹ቆይ…የስልኩን ነገር ምን አልሺኝ?››
‹‹እሺ…አልዘጋውም…ግን ቀጥታ አትደውልልኝ….ለማውራት ስትፈልግ መልእክት ላክልኝ..ከዛ ሁኔታዎችን አመቻችቼ በተቻለኝ ፍጥነት ደውልልሀለው››
‹‹ተስማምተናል..በይ ቸው››
‹‹ስልኩ ተዘጋ….በጣም ደስ አላት…ነገሮች ሁሉ ባሰበቻው መንገድ እንዲህ መስመር ስለያዙላት ወደላይ አንጋጣ ፈጣሪዋን አመሰገነች፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

21 Jan, 19:22


‹‹ይሄውልህ ልጄ…ልጃችን ያለችውን ለማድረግ እኔም ባለቤቴም ተስማምተናል…..ለዛ ቃል እንገባለን..አንተ ትረዳናለህ እኛም በመሀከላችን ያለውን ችግር እንፈታዋለን..› ‹‹በጣም ጥሩ…በቃ ሁለታችሁም ጋብቻችሁን ለማዳንና በመሀከላችሁ ያለውን መቃቃር ለማስወገድ ከእኔ ጋር አብሮ ለመስራት ፍቃደኛ ከሆናችሁ ሌላው ነገር እኮ ቀላል ነው…ቃል እገባላችኃላው እንወጣዋለን……በፀሎት በደስታ ወደቤቷ እንድትመለስ እናደርጋለን፡፡››

‹‹አዎ ትክክል ነህ…ግን የእኔ ሀሳብ ምን መሰለህ….አሁን ስትደውልልህ ወደ ቤቷ እድትመለስ አሳምናት ..በቃ እኛ ተስማማን አይደል…ከነገ ጀምሮ ከፈለክ ከአሁን ጀምሮ ማድረግ ያለብንን ነገሮች ንገረን እና ማድረግ እንጀምራለን..እሷ ግን ዛሬ ነገ ሳትል ወደቤቷ ትመለስ..እሷ እዚሁ እቤቷ እያለች እኛ ችግራችንን መፍታት እንችላለን››
‹‹ይቅርታ ይሄ መንገድ የሚሰራ አይመስለኝም››አለ ሰለሞን
‹‹ብሩን እኮ እንከፍልኃለን..ማለቴ አምስት ሚሊዬኑን እንከፍልሀለን..አይደል ኃይሌ..?››.ወ.ሮ ስንዱ ለዘመናት አድርገው በማያውቁት መንገድ ባልዬውን በአይናቸውም በቃላቸውም እየተለማመጡ ጠየቁ፡፡
‹‹አዎ..ትክክል ነች…ከፈለክ አሁኑኑ የ5 ሚሊዬኑን ቼክ ልፅፍልህ እችላለው…አዎ››
‹‹ይቅርታ እኔ ያልሰራሁበትን ገንዘብ የምቀበል አይነት ሰው አይደለሁም…በዛ ላይ 5 ሚሊዬኑን ከፍልሀለው አለች እንጂ እኔ ስራዬን እሷ ባለችው መንገድ እንኳን በውጤት ባጠናቅቅ…ይሄንን ብር እቀበላለሁ አላልኩም..እኔ ለሰራሁት ስረ የሚገባኝን ብር ብቻ ነው እንዲከፈለኝ ምፈለገው..እኔ እናንተን ብሆን ግን ሁሉን ነገር ልጃችሁ ባለችው መንገድ እንዲከናወን ጊዜ ሳላባክን እንቀሳቀስ ነበር….ቢያንስ እኮ እነዚህን እናንተ የምትሉትን ነገር ለልጃችሁ አቅርቤ የምትለውን ለመስማት የተወሰነ ቀናቶች ሞክረን እናንተ ግንኙነታችሁን ለማሻሻል የምታደርጉትን ጥረት አይተን ጥረቱ ፍሬ እያፈራ መሆንኑ መመዘን አለብን…እኔ ባለሞያ ነኝ..በፀሎት ደግሞ ዋና ቀጣሪዬ ነች..ታማኝነቴ ለእሷ ነው….እሷ ባለችው መንገድ ለመጓዝ ስትወስኑ ደውሉልኝ..አሁን ልሂድ..ብሎ ከመቀመጫው ሲነሳ ሁሉቱም በድንጋጤ ከተቀመጡበት ተስፈንጥረው ተነሱና ግራና ቀኝ ትከሸውን ይዘው መልሰው አስቀመጡት..
‹‹እሺ በቃ እንዳልክ ይሁን..አሁን ማድረግ ያለብንን ንገረን..ምንም ጊዜ ሳናባክን ወደተግባር መግባት አለብን፡፡ለመሆኑ ምን ያህል ጊዜ የሚፈጅ ይመስልሀል?፡፡››
‹‹ወር ..ሁለት ወር..ወይም ሶስት ወር..ወይም አመት››
‹‹አልገባኝም?››አቶ ኃይለልኡል ኮስተር ብለው ጠየቁ
‹‹ጊዜውን ምታረዝሙትም ምታሳጥሩትም እናንተው ናችሁ፡፡የጋብቻ አማካሪ ውጤታማ የሚሆነው ሁለቱ የጋብቻ ተጣማሪዎች በመሀከላቸው ያለውን ችግር ለመፍታት ቁርጠኛ በሆኑበት መጠን ነው…እኔ እገዛ ነው የማደርግላችሁ..ትልቁን ስራ የምትሰሩት እናንተው

ናቸሁ…ምን ያህል ፍቃዳኛ ናችሁ ?ቁርጠኝነታችሁስ…?ችግሩን ለመፍታት ምን ያህል ርቀት ድረስ ትጓዛላችሁ?››
‹‹ነገርንህ እኮ …ልጄ እንድትመለስ እንኳን ከባሌ ጋር ሰላም ማውረድ ይቅርና ከዳቢሎስ ጋርም ተስማሚ ብባል አደርገዋለው…››
‹‹የእኔም አቋም ከእሷ የተለየ አይደለም››
‹‹እንደዛ ከሆነ እንጀምር…ከዚህ ከተማ ለቀንናት እንወጣለን…የፈለጋችሁበት ቦታ መምረጥ ትችላላችሁ ..ላንጋኖ ሰዳሬ ወይም ሌላ ቦታ ከተማና …ግርግር ያለበት ቦታ ግን አይሆንም››
‹‹እሺ..ሌላስ?››
‹‹ስልክ ሁለታችሁም በቀን ለአንድ ሰዓት ያህል ብቻ ነው የምትጠቀሙት…ከምትፈልጉትሰ ሰው ጋር የምትደዋወሉት  በዛ በተፈቀደላችሁ ሰዓት ብቻ ነው….››
‹‹ይሁን እሺ…››
‹‹በቃ ከአሁን ጀምሮ ተዘጋጁ ..ነገ ሶስት ሰዓት አንንቀሳቀሳለን..ቀድሜ ደውልላችኃላው፡፡››
‹‹እሺ..ተስማምተናል፡፡››
‹‹በቃ ደህና ዋሉ…››መቀመጫውን ለቆ ተነሳ…ደስ እያለው እቤቱንም ሰፈሩንም ለቆ ሄደ

ይቀጥላል....

ቻናላችንን  ይቀላቀሉ👇👇

♥️♥️♥️♥️♥️❤️❤️

ከመጽሐፍት መንደር💠

21 Jan, 19:22


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራአምስት

‹ለማንኛውም ተመልሼ መጣለሁ..ና ወደቢሮ እንመለስ …››ብለው ሰለሞንን አስከትለው ወደቢሯቸው ተመለሱ፡፡
‹‹በል አሁን ንገረኝ ልጄ እንዴት ናት?››
‹‹እኔ እንጃ እንዴት እንደሆነች አለውቅም?››

‹‹ማለት ደብዳቤውን ስትሰጥህ አይተሀት የለ..?ከስታለች…እንዴት ነች ተጎሳቁላለች?ልቧስ እንዴት ነው…?ታውቃለህ አይደል የልብ በሽተኛ ነች››
‹‹ደብዳቤውን በአካል መጥታ አይደለም የሰጠችኝ..ማለቴ ቢሮዬ በሚገኝበት ህንፃ መታጠቢያ ቤት አስቀምጣ ስልክ ደወለችና እንድወስድ አዘዘችኝ..ስልኬን ከየት እንዳገኘች አላውቅም…ሁሉን ነገር የተነጋገርነው በስልክ ነው…በወላጆቼ ትዳር መካከል አለመግባባት አለና እርዳቸው ብላ መቶ ሺ ብር በደብተሬ አስገብታለች….መልሼ ስልኳን ብደውልላት አይሰራም…እራሴ ስፈልግህ መልሼ አገኝሀለው ነው ያለችኝ..እኔ የማውቀው ይሄኑን ነው፡፡››
ኪሱ ገባና ቢዝነስ ካርዱን አውጥቶ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠ‹‹ይሄው አድረሻዬ …ቢሮዬ ሜኪሲኮ ኬኬር ህንፃ ላይ ነው….ዝግጁ ስትሆኑ ደውሉልኝ….ካልሆነም ይንገሩኝ ገንዘቡን ተመላሽ አደርጋለው፡፡አሁን ልሂድ፡፡››
‹‹እሺ በቃ…አመሰግናለው..አሁን ተረጋግቼ ማሰብ አለብኝ..ደውልልሀለው፣ልጆቹ ይሸኙሀል››አሉት፡፡
እሱም ሌላ ምንም ተጨማሪ ቃላት ሳይናገር  ቦርሳውን ያዘና ሹልክ ብሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
በሁለተኛው ቀን የሚጠብቀው ቁጥር ተደወለ…የልብ ምቱ ፍጥነት እንደጨመረ እየታወቀው ነው…እንደምንም ለመረጋጋት ሞከረና አነሳው፡፡
‹‹አቤት …..››
‹‹ሃይለ ልኡል ነኝ….››
‹‹አወቅኮት፣ ሰላም ኖት ?››
‹‹ደህና ነኝ….እቤት ብቅ ብትል ይመችሀል?››ሰከን ባለና በተረጋጋ የድምፅ ቅላፄ ጠየቁት፡፡
‹‹መቼ…አሁን››
‹‹አዎ አሁን ብትመጣና ..በአንዳንድ ሁኔታዎች ላይ ብናወራ ደስ ይለኛል››
‹‹እሺ….ከአንድ ሰዓት በኃላ እደርሳለሁ..››
‹‹አመሰግናለሁ….ከባለቤቴ  ጋ ሆነን እንጠብቅሀለን››

‹‹ጥሩ በቃ መጣሁ….››ስልኩን ዘጋና ቀጥታ ቦርሳውን ይዞ ከመቀመጫው ተነሳ….ወደፊት ለፊተኛው ክፍል ሲገባ ለሊሴ ፊትለፊቷ ያለውን ኮምፒተር ከፍታ አፍጥጣ ነበር….
‹‹ልወጣ ነው…ዘሬ ተመልሼ የምመጣ አይመስለኝም››
‹‹እሺ በቃ..ባለጉዳይ ከመጣ…ለነገ ቀጠሮ ይዤላቸዋለው››አለችው፡፡
‹‹ጥሩ እንደዛ አድርጊ….መልካም ውሎ››ብሏት ቢሮውን ሙሉ በሙሉ ለቆ ወጣ፡፡
መኪናውን እራሱ እያሽከረከረ….አእምሮውም በሀሳብ እየተሸከረከረ ቀጥታ ወደአቶ ኃይል ልኡል ቤት ነዳው…ምን እንደሚጠብቀው አያውቅም..እርግጥ ና ብለው ሲጠሩት በጣም በተረጋጋ እና በተለሳለሰ ድምፅ ነው…ግን ያንን ያደረጉት ሁሉ ነገር ሰላም ነው ብሎ በማመን በገዛ እጁ ሄዶ እጅ እንዲሰጣቸው አስበው ከሆነስ? ይሄ የእቅዳቸው አንዱ አካል ቢሆንስ?››እራሱን ደጋግሞ ጠየቀ…በሀሳብ ከመብሰልሰል ለደቂቃ እንኳን ሳያነጥብ ሰፈራቸው ደረሰ …መኪናውን ከሩቅ አቆመና ደወለ፣ስልኩ ተነሳ››
‹‹ኪያ እንዴት ነሽ?››
‹‹ሰልም ነኝ….አንተስ?››
‹‹አለው…እዛ የነገርኩሽ ቦታ ጠርተውኝ እየሄድኩ ነው››
‹‹የት?››
‹‹አንቺ ደግሞ …የጠፋችው ልጅ ወላጆች ጋር ነዋ››
‹‹ና ብለው ጠሩህ?››
‹‹አባትዬው አሁን ጠርተውኝ በራፋቸው ጋር ደርሼ ወደውስጥ ዘልቄ ከመግባቴ በፊት መኪናዬን አቁሜ ነው የምደውልልሽ››
‹‹ምነው ፈራህ እንዴ?››
‹‹አይ ለምን ፈራለሁ….ማለቴ ከገባሁ በኃላ በፀጥታ ከእነሱ ጋር ለመነጋገር ስልኬን ስለማጠፋ ድንገት ደውለሽ ስልኬ ካልሰራልሽ እንዳታስቢ ብዬ ነው››
‹‹አይ ጥሩ አደረክ…ለማንኛውም እንደወጣህ ደውልልኝ››

‹‹እሺ….ኪያ …ቸው››ስልኩን ዘጋ፡፡ቀለል አለው፡፡‹‹ቢያንስ አሁን እዛው በገባሁበት ከቀረሁ በቀላሉ አድርሻዬን ታገኘዋለች፡፡››ብሎ አሰበና መኪናውን አንቀሳቀሰ….የውጭ በራፍ ጋር ደረሰና ክላክሱን አንጣረረ….ወዲያው በራፉ ተከፈተና…ጠብደል ጥቁር ሱፍ የለበሰ ጠባቂ ወደእሱ መጣና …ማንነቱን ጠየቀው‹‹አዎ አንተን እየጠበቁሀ ነው››ብሎት መልሶ ሄደና በራሀፍን ከፈተለት ….ወደውስጥ ዘልቆ ገባና ከአራት መኪና በላይ ወደቆመበት ገራዥ በመሄድ ክፍት ቦታ ፈልጎ መኪናውን አቆመና ሞተሩን አጥፍቶ ወረደ…..ጠባቂው እየመራ ሳሎን በራፍ ድረስ ወሰደውና ወደኃላ ተመለሰ…
እራሳቸው አቶ ኃይለልኡል ነበሩ በራፍ ድረስ መጥተው በወዳጅነት አቀባበል አቅፈው የተቀበሉት….ወደሳሎን ይዘውት ዘለቁ…መጀመሪያ ምግብ እንብላ…‹‹እስከአሁን ቁርስ ሳንበላ እየጠበቅንህ ነው››አሉት፡፡
‹‹ዝም ብላችሁ ተቸገራችሁ….እኔ እኮ በልቼ ነበር የመጣሁት››
‹‹ቢሆንም…ና ቁጭ በል….››ቀድመው ተቀመጡና የሚቀመጥበትን ቦታ አሳዩት…ተቀመጠ
‹‹ልጇች..ስንዱን ጥሯት››
ሰራተኞቹ ግራ የገባቸው ይመስል ዝም ብለው ሰውዬው ላይ አፈጠጡ፡፡
‹‹ምን አፍጥጣችሁ ታዩኛላችሁ…ክፍሏ ነች…አንዳችሁ ሂዱና እንግዳው መጥቷል ነይ በሏት…የተቀራችሁ ቁርሱን አቅርቡ››
ሁሉም ትዛዙን ሰምተው ተበታተኑ
‹‹እንዴት ነው …ወ.ሮ ስንዱ ተሸላቸው?፡፡››ሰለሞን ጠየቀ፡፡
‹‹አዎ…እድሜ ላንተ የልጃችንን ሰላም መሆን ዜና ካሰማሀን በኃላ ተሸሏታል…የተሳሰረ የነበረ እግሯቾም ታምራዊ በሆነ ፍጥነት ተላቀውላት አሁን በራሷ መራመድ ችላለች፡፡››
‹‹በእውነት በጣም እስደሳች ዜና ነው…ያልኳችሁን ስላመናችሁኝ ደስ ብሎኛል››
‹‹አይ እሱ እንኳን በቀላሉ አላመንህም…ስላአንተ ለሁለት ቀን ሳስጠና ነበር…በዛ ላይ ከእሷ ጋር የተደዋወላችሁትን የስልክ ልውውጥ አግኝቼ አዳምጬዋለው…የልጄን ድምፅ ሰምቼያለው…በሰላምና በጤና መኖሯን ያረጋገጥኩት ከዛ በኃላ ነው…በቀላሉ ላምንህ

ሳላልቻልኩ ይቅርታ….ደግነቱ እንዲህ በቀላሉ እንደማላምንህ ልጄ አስቀድማ ነግራሀለች…ይገርማል ይሄን ያህል ጠልቃ ምታውቀኝ አይመስለኝም ነበር››
‹‹ልጆት አይደለች…ልጆች እኮ ወላጆች የሚያደርጉትን እያንደንዱን ድርጊት በጥልቀት ያስተውላሉ ፣በአእምሮቸውም ይመዘግባሉ…ስለወላጆቻቸው በጥልቀት ነው የሚያውቁት››
‹‹ትክክል ነህ ..››ንግግራቸውን በወ.ሮ ስንዱ መምጣት ምክንያት አቆረጡ….ሰሎሞን ከመቀመጫው ተነስቶ በትህትና ሰላምታ ተቀበላቸው….ወንበር ስበው ተቀመጡ..ቁርስ ቀረበ….ጠረጴዛው ሙሉ ቢሆንም ያን ያህል አፒታይት የነበረው ሰው አልነበረም….ቁርሱ እንደተጠናቀቀ ከወንበራቸውን ተነስተው አንደኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኘው የአቶ ኃይለልኡል ቢሮ ተያይዘው ሄዱ.. ወደሶፋው ሄዱና ተቀመጡ..፡፡
‹‹እንግዲህ አሁን መነጋገር እንችላለን››አቶ ኃይለልኡል ጀመሩ
ወ.ሮ ስንዱ ተቀበሏቸው‹‹ልጄ እንደው አባክ እርዳን ..ልጃችን ወደቤቷ እንድትመለስ አሳምናት››ከመቀመጫቸው ተነስተው እግሩ ላይ ሊደፉ ሲሉ በአየር ላይ ትከሻቸውን ያዘና መልሶ አስቀመጣቸው፡፡
‹‹አይገባም..እኔ እዚህ ያለሁት እኮ ልረዳችሁ ነው..የእኔም ምኞትና ፍላጎት ያ ነው››
‹‹እኮ አድርገዋ….ያለችበትን እንድትነግርህ አሳምናት›››
‹‹አይ በእንደዛ አይነት ሁኔታ እንኳን ምትስማማ አይመስለኝም..እሷ ወደቤቷ ምትመለስበትን አንድና ብቸኛ መንገድ በግልጽ ተናግራለች…ምንም አይነት ችግር ሳይፈጠር ደስተኛ ሆና ወደቤቷ እንድትመለሰ ያለችውን አድርጎ ማሳየት ብቻ ነው ያለብን፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

20 Jan, 19:03


ድረስ ስሄድ አሜን ብሎ የሚቀበልለኝ ይመስልሻል?ያለሽበትን ቦታ በትክክል የማውቅ ነው የሚመስለው…ሊያሳስረኝም ሆነ ሌላ ነገር ሊያደርገኝ ይችላል….ያንን አስበሽዋል?፡፡››
‹‹አይ አባቴን አውቀዋለው..እንደዛ አያደርግም…መጀመሪያ እርግጠኛ ለመሆን ያሰልልሀል..ስትገባ ስትወጣ ከማን ጋር እንደምትገናኝ ምን አይነት ሰው እንደሆንክ ያጣራል
፣ስልክህን ያስጠልፋል…ይሄንን የተነጋገርነውን ሁሉ ከቴሌ አስወጥቶ ያዳምጣል…ከዛ እኔ ልጅ በዚህ ነገር እንዴት እንደቆረጥኩ እርግጠኛ ይሆንና ከአንተ ጋር ይተባበራል..ወይም እኔን ልጁን እስከወደያኛው ይሰናበታኛል፡፡››
‹‹ገባኝ…በእውነቱ ሁኔታዎች በጣም ቢያስፈሩኝም …ግን እምቢ ልልሽ አልችልም….ተስማምቼለው፡፡››
‹‹ጥሩ በቃ ያልኩህን አድርግ..የባንክ ቁጥርህን ላክልኝ…ደብዳቤውን ነገ እንዲደርስህ አደርጋለው…ከዛ ሁኔታዎችን አመቻችና እናትንና አባቴን አግኛቸው……….ከዛ በኃላ ያሉትን ነገሮች እንነጋገራለን፡፡››
‹ጥሩ እንዳልሽ…ስፈልግሽ በዚህ ቁጥር ነው የማገኝሽ?››
‹‹አይ አንተ ልታገኘን አትችልም..እኔ ነኝ የማገኝህ…ቸው››ስልኩ ተዘጋ፡፡
አሁንም እንደደነዘዘ ነው፡፡የባንክ ሂሳብ ቁጥሩን ላከላት…ከአንድ ሰዓት በኃላ እንዳለችው 100 ሺ ብር እንደተላከለት በስልክ ቁጥሩ ሚሴጅ መጣለት…አሁን የበለጠ ብርድ ብርድ አለው…
‹‹ሠሎሞን ምን አይነት ነገር ውስጥ እራስህን እያስገባህ ነው?፡፡››ጠየቀ…መልሶ ድህረ ገፅ ላይ ገባና የበፀሎትን የተለያ ፎቶዎችን ዳውንሎድ አደረገ ፣እንዲህ አይነት የተሰወሳሰበ ነገሮችን አስባ ለመከወን የምትንቀሳቀስ ሳይሆን ቢነግሯት እንኳን የማዳመጥ ትግስት ያላት አትመስልም፡፡እያንዳንዱን ፎቶ በየተራ እየገለጠ ተመለከት...ወርቃማ ፀጎሯን..ጥቋቁር አይኖቾን ..አፍንጫዋንና የሚያጎጉ ብስል እንጆሪ መሳይ ከንፈሮቹን አንድ በአንድ ነጥሎ ለየብቻ አጠናቸው…ይሄንን ጉዳይ ብቻውን አመንዥጎ ሊወጣው ስለማይችል አስቴር ጋር ደወለ….ቤት ነኝ ስትለው….ጃኬቱን ከተሰቀለበት አንስቶ በእጁ እንዳንጠለጠለ ሄደ፡፡

///
በማግስቱ
በፍራቻ እንደተሸበብ የሆንኩትን ልሁን በሚል ስሜት የውስጥ ፍራቻውን እና ስጋቱን በላይ ገፅታው መኮሳተር ሸፍኖት የአቶ ኃየለ መለኮትን ቤተመንግስት መሰል ግዙፍ ህንፃ መጥሪያ ተጫነ….ብዙም ሳይቆይ የጠቅላይ ሚኒስትሩን ጋርድ የሚመስል ሙሉ ጥቁር ሱፍ የለበሰ ጠብደል ወጣት በራፍን ከፈተና‹‹አቤት ጌታዬ ምንድነበር?››አለው፡፡
ከስር እስከ ላይ አየውና ሁኔታውን ገመገመ..ይሄን የመሰለ ዘናጭ መለሎ የዚህ ቤት ዘበኛ እንዳይሆን ብቻ ሲል አሰላሰለ…ከላይ ወደታች አፍጥጦ እያየው እንደሆነ ሲገባው ወደቀልቡ ተመለሰና ‹‹አቶ ኃይለመለኮትን ወይም ባለቤታቸውን ፈልጌ ነበር››
‹‹ቀጠሮ አላህ?››
‹‹አይ የለኝም››
‹‹ይቅርታ ጌታዬ …እንደዛ ከሆነ ልታገኛቸው አትችልም…አሁን ባሉበት ሁኔታ ምንም አይነት እንግዳ አያስተናግዱም››
‹‹ይገባኛል..የእኔ ጉዳይ ግን የተለየ ነው፡››
‹‹ጌታዬ የተግባባን አይመስለኝም….መልዕክት ካለህ ስጠኝና ላድርስልህ..አስፈላጊ ከሆነ እራሳቸው ደውለው ያገኙሀል..ከዛ ውጭ አዝናለሁ ልረዳህ አልችልም››ብሎ ከእሱ መልስ ሳይጠብቅ የከፈተውን በራፍ መልሶ ሊጠረቅምበት ሲል እጁን በፍጥነት ዘረጋና አስቆመው…
ዘበኛው‹‹ይበልጥ በንዴት አፈጠጠበት››
‹‹አልተረዳሀኝም..ጉዳዬ ከበፀሎት ጋር የተገናኘ ነው..ምን መሰለህ..››
ንግግሩን ሳይጨርስ እጁን ጨመደደና ወደውስጥ ጎትቶ በማስገባት በራፉን ቀረቀረው፡፡
‹‹በጸሎት ምን..?ያለችበትን ታውቃለህ..?የት ነች..?››
‹‹ቀጥታ አባቷን ወይ እናቷን ነው ማናገር የምፈልገው››

‹‹እሺ ና ግባ›› እየተሸቆጠቆጠ ፊት ለፊት እየመራ ወደግዙፉ ሳሎን ይዞት ገባ…እቤቱ ግዝፈትና ሰው አልባ ስለሆነ ያስፈራል…‹‹እባክህ እዚህ ሶፋ ላይ አረፍ በል …ጋሼን አናግሬያቸው መጣሁ…፡፡››ብሎ መልስ ሳይጠብቅ የፎቁን መወጣጫ የሩጫ ያህል እየተራመደ ወደላይ ወጣ….እዛው በቆመበት የቤቱን ዙሪያ ገባ እየጎበኘ በመደነቅ ላይ ሳለ ነበር ልጁ ተመልሶ የመጣው
‹‹ተከተለኝ ጋሼ ቢሯቸው ናቸው..አስገባው ብለዋል..እየጠበቁህ ነው››
በፍጥነት ደራጃውን ወጣና ደረሰበት፡፡ የመጀመሪያውን ፎቅ እንደወጡ ወደግራ ታጠፈና በኮሪደሩ የተወሰነ ከተራመዱ በኃላ በግራ በኩላ ካለው ገርበብ ያለ ክፍል እንዲገባ በእጁ ጠቆመውና እሱ ወደኃላ ዞሩ የመልስ ጉዞ ማድረግ ጀመረ..ሰለሞን ወደ ክፍሉ ተጠጋና በእጁ ቆረቆረ…አሁንም ሰውነቱ እየተንቀጠቀጠ እንደሆነ ይሰማዋል..ወዲያው በራፉ ተከፈተና አንድ ባለግርማ ሞገሳም ግዙፍ አዛውንት ፊት ለፊቱ ቆመው እጃቸውን ለሰላምታ ሲዘረጉለት አገኘ…በደመነፍስ እጁን ዘረጋና ጨበጣቸው …
‹‹ግባ ›› አሉን እጁን እንደያዙ ወደውስጥ ይዘውት ዘለቁ…ከጠረጴዛቸው ፊት ለፊት ካለው ሶፋ ቅድመው ተቀመጡና ፊትለፊታቸው እንዲቀመጥ በእጃቸው ጠቆሙት...
ቦርሳውን ከትከሻው ላይ አወርዶ ፊት ለፊቱ ጠረጴዛ ላይ አስቀመጠና… ተቀመጠ፡፡
‹‹እሺ፣ስለ በፀሎት የምታውቀው ነገር እንዳለ ነበር የተነገረኝ ..?››
‹‹ትክክል››
በመርማሪ  አይናቸው  ከስር  እስከላይ  እየገመገሙት‹‹ለመሆኑ  ልጄን  የት  ነው ምታውቃት?››ሲሉ ጠየቁት
‹‹አላውቃትም››
‹‹አልገባኝም..እሺ ያለችበትን ታውቃለህ?››
‹‹አይ አላውቅም፡፡››
‹‹ሰውዬ እኔ አሁን ቀልድ ላይ ያለው ይመስልሀል?››እንደቆሰለ ነብር ተቆጡ፡፡

‹‹ይረጋጉ፣እሷን ለማግኘት የሚጠቅሞትን ነገር ነው ይዤሎት የመጣሁት››አለና ጠረጴዛ ላይ ያለውን ቦርሳውን ወደራሱ ስቦ በመክፈት ከውስጡ ሁለት የታሸገ ፖስታ አወጣና አቀበላቸው..አገላብጠው አዩት ፣ለአባዬ እና ለእማዬ ይላል..የልጃቸው የእጅ ፅሁፍ ነው፡፡ከመቀመጫቸው በደስታ ብድግ አሉ ፣ ወዲያው ፖስታውን ሸርክተው ቀደዱትና ውስጡ ያለውን ደብዳቤ አውጥታው እዛ ክፍል ውስጥ ከውዲህ አዲያ እየተሸከረከሩ አነበቡት
‹‹ወይኔ ፈጣሪ…ልጄ በህይወት አለች….ልጄ በህይወት አለች..ወደሰሎሞን ተንደረሩን ከተቀመጠበት ጎትተው አቆመትና እያገላበጡ ጉንጩን ሳሙት፤ ጨምቀው አቀፉትና ከግራ ወደቀኝ ወዘወዙት፣‹‹ቆይ አንዴት ናት? ››እጁን ያዙትና የጎተቱ ከክፍሉ ወጡ… ግራ ገባው፡፡ ብዙ ክፍሎችን አልፈው የሆነ ክፍል ከፈቱን ይዘውት ገቡ…ግዙፍ መኝታ ቤት ነው..ፊት ለፊት ያለው ግዙፍ አልጋ ላይ ተዘርረው የተኙ ግዙፍ ሴትዬ አሉ፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

20 Jan, 19:02


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራአራት

ሰላሞን የሆነ ሰው እየተጫወተበት እንደሆነ ነው የተረዳው‹‹ግን ማን ነው እንዲህ ያለ ጫወታ ከእኔ ጋር ለመጫወት የሚደፍረው?››በዙሪያው ያሉ ሰዎችን እያሰበ እራሱን እስኪያመው ቢያስጨንቅ በዙሪያው ካሉ ሰዎች እንዲህ መላ ቅጡ የጠፋበት ቀልድ ከእሱ ጋር ለመቃለድ የሚሞከር ሰው ሊመጣለት አልቻለም፡፡
ነገሩ ቀልድ እንዳልሆነ የተረዳው ልክ በተነገረው መሰረት ከሶስት ቀን በኃላ ተመሳሳይ ስልክ ሲደወልለት ነው፡፡በጉጉት አነሳው፡፡‹‹ሄሎ..አወቅከኝ?››
‹‹መሰለኝ… አደናጋሪዋ ልጅ ነሽ አይደል?››
‹‹መሰለኝ….የባንክ ቁጥርህን ላክልኝ?››
‹‹ምን ለማድረግ?››
‹‹በተነጋገርነው መሰረት ስራ ማስጀመሪያ መቶ ሺ ብሩን እንድልክልህ ነዋ››
‹‹እንዴ? ስራው ምን እንደሆነ ሳላውቅ…ልስራው አልስራው መወሰን የምችለው እኮ ስራውን ሳውቅ ነው…መጀመሪያ በአካል ተገናኝነተን ስለስራው ማውራት አለብን››
‹‹ለጊዜው በአካል ላገኝህ አልችልም…ስራው በአባትና እናቴ መካከል ያለውን ችግር መቅረፍ ነው…እናትና አባቴ ያለፉትን 28 አመታት በጋብቻ አሳልፈዋል….እኔ ሀያ አንድ አመቴን ጨርሼ 22 ዓመት ውስጥ ነኝ…በእድሜዬ አንድም ቀን ሰላም ሆነው አይቻቸው አላውቅም…መኝታ  ለይተው  በየራሳቸው  መኝታ  ቤት  ነው  የሚያድሩት….ሁል  ጊዜ

እንደተጣሉና እንደተጨቃጨቁ ነው.ከዛም አልፎ አንዱ ሌለኛውን ለማስወገድም እስከመፈለግ የሚያደርስ ጥላቻ በመካከላቸው አለ..ወይ አይፋቱ ወይ እንደሰው የእውነት አብረው አይኖሩ፣….እና የፈለኩህ ይሄንን የሻገተና የበሰበሰ ጋብቻ የበሰበሰውን ቅጠል ከላዩ አራግፈህ የደረቀውን የጋብቻ ግንድ ቆርጠህ ከስር አዲስ የፍቅር ቅርንጫፍ እንዲያቆጠቁጥ እንድታደርግ ነው…ቢያንስ እንደባለትዳር መልሰው መተቃቀፍ ባይችሉ እራሱ እንደጓደኛሞች እንዲጨባበጡ ማድረግ እንድትችል ነው፡፡ይሄ ጉዳይ የእኔ የህይወቴ ትልቁ አላማ ነው…እባክህ ይሄንን ጉዳይ እንደጉዳይህ ልትይዘው ትችላለህ….?›››
‹‹በእውነቱ ከጠበቅኩት በተቃራኒ የሆነ መሳጭ ነገር እየነገርሺን ስለሆነ ቀልቤን ገዝተሸዋል…የምትይውን በደንብ እየተከታተልኩሽ ነው፡፡፡ለመሆኑ እኔን የምታናግሪው አባትሽ ወክለሽ ነው ወይስ እናትሽን…..?ማለት እኔን ለስራው እንድታናግሪኝ የጠየቀሽ ማን ነው?፡፡››
‹‹በእውነቱ ሁለቱም ስለዚህ ጉዳይ የሚያውቁት ነገር የለም….››
‹‹ይሄ ደግሞ ነገሩን ይበልጥ ውስብስብ ያደርገዋል..እሺ ቆይ ለመሆኑ እኔን ለምን…?እንዴት እኔን መረጥሽ?››
‹‹ለጊዜው ማንነቱን ልነግርህ የማልችለው አንድ አንተን የሚያውቅ ሰው ነው ሰለአንተ በሆነ ጉዳይ አንስተን ስንጨዋወት በጋብቻ ጉዳይ ላይ እንደምትሰራና በጉብዝናህም እንደሚተማመንብህ የነገረኝ..እንዳአጋጣ ሚ ሆኖ ደግሞ ያንን ሰው እኔ አምነዋለው…እሱ ጎበዝ ነህ ካለህ ጎበዝ ነህ ማለት ነው…ተመለሰልህ?፡››
‹‹በከፊል አዎ…ግን እንደነገርሺኝ በወላጆችሽ መካከል ያለው ችግር ለረጅም አመት የተከማቸ የተወሳሰበና ዘርፈ ብዙም ነው፡፡››
‹‹በትክክል ገልፀኸዋል››
‹‹ችግሩ ምን መሰለሽ..በቀደም እንደነገርኩሽ አንድ የጋብቻ አማካሪ በጋብቻ መካከል የተፈጠረ ችግርን ለመፍታት የሚችለው ሁለቱም ተጋቢዎች በመሀከላቸው ችግር እንዳለ አምነው ያንን ለማስተካከል ከአማካሪው ጋር ለመተባበር ሙሉ ፍቃደኛ ሲሆኑ ብቻ ነው…አሁን ያንቺን ጉዳይ ስንመለከት ወላጆችሽ ጉዳዩን እንኳን አያውቁትም..ቢያውቁትም ፈፅሞ ከእኔ ጋር ለመስራት ላይቀበሉት ይችላሉ.››.

‹‹እሱን ለእኔ ተወውና አሁን የባንክ ቁጥርህን ላክልኝ… ገንዘቡን ትራንስፈር ላድርግልህ››
‹‹ይሄውልሽ ፣እኔ በነገርሺን ታሪክ በጣም ተስቤያለሁ…አንድ ወጣት ሴት በወላጆቾ ግንኙነት ተረብሻ እንዲህ ነገሮችን ለማስተካከል ስትጥር እኔም የበኩሌን እገዛ ለማድረግ ፍጽም ፍቃደኛ ነኝ..እዚህ ላይ ዋናው ገንዘብ አይደለም.. እሱ በሁለተኛ ደረጃ የሚመጣ ነው…አሁን መጀመሪያ አንቺ ራስሽ ወላጆችሽን ከቻልሽ አንድ ላይ አስቀምጠሸ ካልሆነም ለየብቻ ያሰብሽውን ንገሪያቸውና ለማሳመን ሞክሪ..እነሱ ፍቃደኛ ከሆኑ በኃላ ደውይልኝ..ከዛ ፕሮግራም እናወጣና ያለውን ችግር እያየን ለማስተካከል እንሞክራለን፡፡››
‹‹እነሱን በቀጥታ ማናገር አልችልም››
‹‹ለምን?››
‹‹ስሜ በፀሎት ኃይለልኡል ይባላል››
‹‹እሺ በፀሎት…ለምንድነው ወላጆችሽን ማናገር የማትችይው..?እነሱን ማናገር የማትቺይ ከሆነ እንዴት አድርጌ ነው ወላጆችሽን መርዳት የምችለው?››
‹‹ማለት ስሜን የነገርኩህ ስለእኔ የተወሰነ መረጃ እንዲኖርህ ነው..በፀሎት ኃይለልኡል በልና ድህረገፆች ላይ ወይም ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ፈልግ ..ከ30 ደቂቃ በኃላ መልሼ ደውልልሀለው፡፡››አለችና ስልኩን ጆሮው ላይ ዘጋችበት፡፡
ስልኩ ቢዘጋም እሱ ግን ስልኩ ላይ እንዳፈጠጠ ነው…የገባው የመሰለው የልጅቷ ሁኔታ መልሶ እየተበታተነበት ነው‹‹…ድህረ-ገፅ ላይ ስለእሷ ምን…?ታዋቂ ሰው ነች ማለት ነው…?››
ጎግል ከፍቶ ››በፀሎት ኃይለመለኮት››ብሎ ሰርች መድረግ ጀመረ..በርካታ መረጃዎች ተዘረገፉ….እውነትም ይህቺ ልጅ ታዋቂ ነች መሰለኝ..ብሎ የመጀመሪያውን ሲያነብ
‹‹የታዋቂ ቢሊዬነሩ የኃይለመለኮት ብቸኛ ወራሽ በውድቅት ለሊት ከቤት ወጥታ ከጠፋች 14 ቀን አልፏታል፡፡››
‹‹ታዋቂው ቢሊዬነር ብቸኛ ልጅ በፀሎት ለምን ከቤቷ ጠፋች?››
‹‹በጸሎት ኃይለመለኮትን ያለችበትን የጠቆመ የ5 ሚሊዬን ብር  ሽልማት እንደሚሸልሙ አባቷ ለፋና ቴልቨዥን በሰጡት መግለጫ አሳወቁ››
በሚያነበው ዜና ሁሉ ደነዘዘ…..ማንበቡን አቆመና..ደወለላት
‹‹ሄሎ ..››
‹‹አሁን በመጠኑ ገባህ?››
‹‹ማለት አሁንም እንደጠፋሽ አይደለሽም አይደል…..?ማለቴ ወደቤት ተመልሰሻል?››
‹‹አይ  አልተመለስኩም…ወደቤት  እንድመለስም  እንደወጣው  በዛው  እንድቀርም የምታደርገኝ አንተ ነህ፡፡››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ከእቤት የጠፋሁት የወላጆቼ ጭቅጭቅና የእርስ በርስ ጥላቻ ምርር ብሎኝ ነው….እኔ የእነሱን ሀብታቸውንም ሆነ ውርሳቸውን አልፈልግም፡፡ እኔ የምፈልገው ፍቅራቸውን ነው..ቢያንስ የሁለት ጓደኛሞችን አይነት እርስ በርስ የመግባባት እና የመረዳዳት ደረጃ ላይ እስኪደርሱ ወደዛ ቤት አልመለስም…እና እቅዴ ምን መሰለህ..ለእነሱ ደብዳቤ ፅፌ ልክልሀለው….በዛ ደብዳቤ ላይ ግልፅ የሆነ ፍላጎቴን አሰፍራለሁ…ማለቴ በግልፅ ከአንተ ጋር ሰርተው በማሀከላቸው ያለውን ግንኙነት ካስተካከሉ…እናም ያንን አንተ ካረጋገጥክልኝ ወደቤት እመለሳለው..ካለበለዚያ በቃ እኔም እነሱን እረሳለው አነሱም እኔን ይረሱኛል ማለት ነው፡፡››
‹‹በተሰቀለው..ነገሩ ካሰብኩት በላይ የተወሳሰበና ..አደገኛም ጭምር ነው፡፡››
‹‹ለዚህ እኮ ነው አምስት ሚሊዬን ብር እንድታገኝ የማደርግህ..ግብቷሀል አይደል አባቴ እኔን ላገኘ ወይም ያለሁበትን ለጠቆመ ሰው የ5 ሚሊዬን ብር ሽልማት አዘጋጅቷል ..ያ ማለት ነገሮች እንደተሳኩ እርግጠኛ በሆንኩ ጊዜ አንተ እንድታገኘኝና ለቤተሰቦቼ እንድታስረክበኝ አደርጋለሁ…እናም ለሽልማት የተዘጋጀውን ብር ከአባቴ ተቀብዬ ለአንተ አስረክብሀለው፡፡› ‹‹ገባኝ..አሁን እኔን ያሳሰበኝ የብር ጉዳይ አይደለም..አስበሽዋል ግን በጠቅላላ በሀገሪቱ ጉራንጉር እየተፈለግሽ ነው…በጥቂቱ እንደተረዳሁት አባትሽ እጅግ ተፅዕኖ ፈጣሪና የፈለገውን ማድረግ የሚችል ሰው ነው…እንዳልሽው ለእነሱ የፃፍሺውን ደብዳቤ ይዤ እቤት

ከመጽሐፍት መንደር💠

20 Jan, 16:33


ይህንን ያውቃሉ⁉️

አይጦች በጣም በብዛትና በፍጥነት ከሚወልዱ እንስሳቶች መካከል ግንባር ቀደም ሲሆኑ አንዲት አይጥ ከ 21-23 ቀን ባለው ግዜ ውስጥ አርግዛ በአንድ ግዜ በርካታ ልጆችን  ትታቀፋለች .... ለምሳሌ ቤታችሁ 5 ለአቅመ ሄዋን የደረሱ አይጦች ቢኖሩና እንደፈለጉ እየበሉ አመቱን ቢቆዩ እርስ በእርስ እየተፈላፈሉ በአመት ውስጥ ብቻ ከ 1,270,500 በላይ አይጦች ሊደርሱ እንደሚችሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ 🎧

ከመጽሐፍት መንደር💠

19 Jan, 06:48


እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ

መልካም በዓል !

ከመጽሐፍት መንደር💠

15 Jan, 17:53


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራ ሶስት

እለቱ እሁድ ነው፡፡ከፊራኦል ጋር ለመውጣት ስለተነጋገሩ እየተዘጋጀች ነው፡፡ለሊሴ እየረዳቻት ነው፡፡
ሰው ከለገመ ከሻማ በላይ በቀላሉ ቀልጦ የሚጠፋ ከጠነከረ ደግሞ ከአልማዝም በላይ ማይቆረጥና ማይሸረፋ ተአምራዊ ፍጡር መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡በፀሎትም የማያልፍ የመሰላት አሰቃይ ህመም በጥቂት ቀናት ውስጥ ጥሏት ሄዶ ንፅህና ጤነኛ ልጅ ሆናለች፡፡የእግሯን ስብራት ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ድኗል…የፊቷ ቁስል ግን ምንም እንኳን ቢድንም ጣባሳውና ቁስለቱ አሁንም በግልጽ ፊቷ ላይ ይታያል… በዚህ ምክንያት አሳባ ከፊል ፊቷን ሁሌ በሻርፕ እንደሸፈነችው ነው፡፡ዋና ምክንያቷ ግን ማንነቷ በቀላሉ እንዳይለይ በማሰብ ነው፡፡አሁንም ተመሳሳይ አለባበስ አድርጋ በዛ ላይ ጥቁር መነፅር አይኗ ላይ ሰክታ ዝግጁ ሆነች፡፡
‹‹ግን እህቴ ለምንድነው እኔን የማታስከትሉት?››ለሊሴ ተነጫነጨች፡፡
‹‹አይ …መጀመሪያ ከወንድሜ ጋር የምንሄድበት ቦታ አለ…ባይሆን ከዛ ቶሎ ከጨረስን እንደውልልሽና ትቀላቀይናለሽ››
‹‹ይሁንላች ግን ታበሳጭቼባችኋለሁ››
በታክሲ ከሰፈር ሁለት ፌርማታ ያህል ርቀው ከሄዱ በኃላ ‹‹ደርሰናል እንውረድ›› አላት፡፡ያን ያህል ቅርብ ይሆናል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡እንደወረዱ ቀጥታ ፊት ለፊት የሚገኝ በፅድና በባህርዛፍ አፅድ የደመቀ ሰፊ መናፈሻ ውስጥ ነው ይዞት የገባው…ቀጥታ ከሰው ነጠል ያለ ቦታ ይዞት ሄደና ቁጭ እንድትል መቀመጫ አመቻችቶላት ከፊት ለፊቷ ተቀመጠ‹‹እሺ ምን ትጠቀሚያለሽ?››
‹‹ቆይ እስኪ… ምን አስቸኮለህ…መጀመሪያ ትምጣ››
‹‹ማን?››
‹‹ምን ….ማንን ልናገኝ ነው የመጣነው…?ፍቅረኛህ ነቻ…በል ደውልላት፡፡››
‹‹ስልክ የላትም››
‹‹ታዲያ እንዴት ነው የምታገኘን››
‹‹የልቤን ምት አዳምጣ ትመጣለች››
‹‹ጥሩ ትቀልዳለህ….ይሄ የተለመደ መገናኛ ቦታችሁ ነው ማለት ነው…ገባኝ›› አስተናጋጁ መጣችና‹‹ምን ልታዘዝ ?››ብላ ጠየቀች፡፡
በፀሎት ቀደም ብላ‹‹ሰው እየጠበቅን ነው….››ብላ ለአስተናጋጆ መለሰችላት
‹‹አይ አሷን እንጠብቅም..ቆንጆ ፒዛ አሰሪልን…ፒዛው እስኪደርስ እሷም ትደርሳለች››

አስተናጋጆ ትዕዛዙን ተቀብላ ሄደች፡፡
ፊራኦል ወደእሷ አትኩሮ እያያት…..‹‹እስኪ ሻርፑን አንሺው››በማለት ያልጠበቀችውን ጥያቄ ጠየቃት
‹‹እንዴ ለምን?››
‹‹ሙሉ ፊትሽን ለማየት ፈልጌ››
‹‹ኖ ዌይ…..›
‹‹ምን ችግር አለው?››
‹‹እኔ  እራሴ  ሙሉ  በሙሉ  ፊቴ  እንደዳነ  እና  እንደማያስጠላ  እርግጠኛ  ስሆን እገልጠዋለው፡፡››
‹አንቺ እንዴት ልታስጠይ ትችያለሽ…ውብ እኮ ነሽ››
‹‹ሙሉ ፊቴን ሳታይ ውብ መሆኔን በምን አወቅክ…?››ኮስተር ብላ በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹እኔ እንጃ ውብ እንደሆንሽ ግን እርግጠኛ ነኝ፡፡››
መልስ ልትሰጠው አፏን ስትከፍት አስተናጋጇ የታዘዘውን ፒዛ ይዛ ፊታቸው ስታስቀምጥ አፏን ያለምንም ንግግር ከደነች፡፡
‹‹‹ለእኔ እስፕራይት አምጪልኝ…..ላንቺስ ?››
‹‹እንዴ ልጅቷ ሳትመጣ….?››
‹‹ባክሽ የሆነ ነገር እዘዢ እሷ ስትመጣ የራሷን ነገር ታዛለች››
ግራ እየገባት አዘዘች …ፒዛውን ቆርሶ መብላት ሲጀምር ፣ በገረሜታ ተከተለችው… በልተው ጨርሰው እንኳን ልጅቷ አልመጣችም››
‹‹እንደዛ  ቅኔ  ምትቀኝላት  ልጅ  እስከአሁን  ካልመጣች  ከአሁን  ወዲያም  የምትመጣ አይመስለኝም፡፡››

‹‹መጣችእኮ››
‹‹የታለች?››
‹‹ይህቹት ፊት ለፊቴ ቁጭ ብላ እያወራቺኝ ነው፡፡››
‹‹እየቀለድክብኝ ነው እንዴ?››
‹‹እሺ አትበሳጪ..እኔ ምንም አይነት ፍቅረኛ የለኝም….አንቺን ወጣ አድርጌ ማዝናናት ስለፈለኩ ነው እንደዛ ያልኩሽ››
‹‹አንተ ውሸታም……..ቆይ ምንም ፍቅረኛ ሳይኖርህ ነው እንደዛ ፈዘህ በውድቅት ለሊት ቅኔ ስትዘርፍ የነበረው››
‹‹በተጨባጭ ፍቅረኛ የለኝም አልኩሽ እንጂ በምናቤ ስዬ የማስባት ሴት የለችም አላልኩሽም…..እንደዛ አወራ የነበረው በልቤ ውስጥ ተንሰራፍታ የተቀመጠችውን ልክ እንደአንቺ ውብ የሆነችውን ልጅ እያሰብኩ ነበር››
‹‹ምን አይነት አዝግ ልጅ ነህ….?እኔ ደግሞ እንዴት አይነት ቆንጆ ልጅ ትሆን እያልኩ ለሊቱን ሙሉ ሳስብና ስጓጓ ማደሬ››
‹‹ምን ያጓጓሻል…የፈለገ ውብ ብትሆን ካንቺ አትበልጥ…አንቺ እኮ ሁለመናሽ ውብ ነው…ማለት ስብዕናሽ ፖስቸርሽ..እርግጠኛ ነኝ መልክሽም ውብ ነው..ፍቅረኛዬ ልክ አንቺን ካልመሰለች ልቤን ማሸነፍ አትችልም››ፊራኦል ቀጥታ መንገር ፈርቶ ነው እንጂ ከበፀሎት ፍቅር ከያዘው ሰነባብቷል…ስሩ ሆና እራሱ ትናፍቀው ከጀመረች ቆይታለች..ለዛ ነው ሙሉ ፊቷን ማየት በጣም የናፈቀው…ቆንጆና ውብ ፊት ነው በምናቡ የሳለው…
‹‹ጥሩ ..ግን ስለውበትና ቁንጅና እኮ በእህትና በወንድም መካከል የሚወራ ኮንሰፕት አይደለም…..ባምርም ባስጠላም እንደእህትህ ነኝ…ለውጥ አያመጣም፡፡››
‹‹እንደእህት እና እህት ግን ይለያያል››
ለዚህ ንግግሩ ምን ብላ መልስ ልትሰጠው እንደምትችል ሊመጣላት አልቻለም…‹‹.እኔ የእህትህን ልብ በውስጤ የተሸከምኩ ሴት መሆኔን ብታውቅ ይሄን ሁሉ ርቀት ለመጓዝ አይዳዳህም ነበር››ስትል በውስጧ አብሰለሰለች

በማግስቱ-----
እቤት ውስጥ ማንም የለም..ሌንሳ ብቻ ከበፀሎት ጎን ቁጭ ብላ እያወራቻት ነው፡፡
እህቴ ስራ በማግኘቴ በጣም ደስተኛ ሆኜያለው….ይገርምሻል ፀሀፊ ሆናለው ብዬ አንድም ቀን ኣስቤ አላውቅም ነበር…››
‹‹ላንቺ እኔ በጣም ደስ ብሎኛል… ስራውን ግን እንዴት ነው..እየለመድሽው ነው? ››
‹‹አሪፍ ነው ..ተመችቶኛል፡፡››
‹‹የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ነው ያልሽው?››
‹‹አዎ እህቴ …ብታይ ሰውዬው ማለቴ አለቃዬ በጣም ነው የሚያሳዝነው፡፡››
‹‹ለምንድነው የሚያሰዝነው? እሱም ፍቅር ይዞታል እንዴ?፡፡››
‹‹አይ እሱን አላውቅም … ያሳዝናል ያልኩሽ…ምንም ደንበኛ የለውም….ዝም ብለን እኔና እሱ ቢሮ ውስጥ ተፋጠን ነው የምንውለው…››ለምን ያሳዝናል እንዳለች ታስረዳት ጀመር፡፡
‹‹ምነው በስራው ጎበዝ አይደለም እንዴ?››
‹‹አረ በቅርብ ነው ከውጭ የመጣው..በሞያው ኤክስፐርት ነው…እንደነገረኝ ከሆነ አሜሪካ እያለ በሞያው ከሶስት አመት በላይ ሰርቶ በጣም ብዙ ሰዎችን ረዳቷል …እዚህ መጥቶ የራሱን ድርጅት ቢከፍትም እንዳሰበው አልሆነለትም….እንደምታውቂው የእኛ ሰው ድብቅ ነው …ባለትዳሮችም ቢሆኑ እዛው ቤታቸው ውስጥ ሲቋሰሉ ይኖራታል እንጂ ገበናቸውን ወደአደባባይ ማውጣት አያስብትም ..ባስ ቢልባቸው እንኳን እዛው የሰፈር ሽማጊሌ ጠርተው በምስክር ፊት ይጨቃጨቃሉ እንጂ ወደባለሞያ አይሄዱም፡፡ለዚህ ጉዳይ ባለሞያም እንዳለው የሚያውቅ የማህበረሰብ ክፍል አንድ ፐርሰንት የሚሞላ አይመስለኝም፡
‹‹ታዲያ እኮ የሰፈር ሽምግልናው ቀላል ነገር አይምሰለሽ…ሁለቱም ለእኛ ጥሩ ያስባል እና ያስማማናል የሚሉትን ሰው በማሀከላቸው አስቀምጠው ችግራቸውን በግልፅ በመነጋገር

ለመፍታት መሞከር ትልቅ ዋጋ ያለው ማህበራዊ እሴታችን ነው፡፡በዚህም መንገድ በጣም በርካታ ሺ ትዳሮች በየአመቱ ስንጥቃቸው ይደፈናል ስብራታቸው ይጠገናል፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

14 Jan, 19:21


ኔግሮ የሚባል ፍሬንድ ነበረኝ ፀባይኛ ነው፣ ሌባ ነው፥ እናቱን ይወዳታል፥ ትምህርት አይገባውም፤ ተንኮል፣ ኳስ ፣ጆተኒ ፣ ትረባ ጎበዝ ነበር።

✔️ በአንድ ሴሚስተር መቶ እና ሁለት መቶ መፅሃፍ ይሰርቃል መቼ? ...እንዴት?...ከማን?... አላውቅም!

መጨረሻ ላይ ውጤቱን እየሳቀ ይነግረኛል።
አንድ ቀን እንኳን ሲሰርቅ ተይዞ አያውቅም !

✔️ የሰረቀውን መፅሐፍ ሲሸጥ አብሬው ሄጄ አውቃለሁ። ከሚገዙት ጋር ደምበኛ እንደሆነ ሰላምታ አለዋወጣቸው ያስታውቃል። አሻሻጡ የሰረቀ ፣ ሳይለፋበት ያመጣ አይመስልም፤ በቸልታ አይደለም። በርጋታ እንደትልቅ ሰው... "አይሆንም...፣ ይቅር...፣በቃ፣ ጨምር " እያለ ነው ።

እናቱን "ሸቅዬ... እዛ ማዶ ያሉት ሃብታም ሰዎች፤ ለእናትህ ስጣት ብለው ብር ሰጡኝ" እያለ እንደሚሰጣት ነገሮኝ ያውቃል ።

ሰባተኛ ክፍል ፣ ስምንተኛ ክፍል እያለን እናቱን ያግዛት ነበር ። ይወዳታል፤ አወዳደዱ እንደትልቅ ሰው ነው። "ማሚዋ ደብሯታል ...አሟታል. . . ገበያ ቀዝቅዞባታል" እያለ ያስብላታል።

ከጓደኛው አይሰርቅም። ለጓደኛው ለኔ ለሚለው ሰው ይሳሳል።

አይኖቹ ትናንሽ ናቸው፣ አካባቢውን በትኩረት ያያል፣ ከወሬ ሁኔታን ያያል። ሌባ መሆኑን ብዙ የሩቅ ሰዎች አያውቁም።

ኔግሮ ቁርንጫጭ ፀጉር ያለው፣ ድቅቅ ያለ ገላ ያለው፣ ሲስቅ ቀጭን ድምፅ የሚያወጣ ልጅ ነበር ።

አንዳንድ ቀን ይፎርፍና ሜዳ ጥግ ውኃ ልኩ ጋር ብቻውን ይሆናል ። ዝም ይላል ኳስ አይጫወትም። ቀጭን ድምፅ እያወጣ የሚስቃት ሳቅ አትኖርም። ለመኮረጅ ብዙ አይሰቃይም።

...ጨዋታ ያበዛል...።

ስለ አባቱ አላውቅም፤ እናቱ ግን ትምህርት ቤታችን በር ጎን ላይ ቃርያ ፣ ቲማቲም፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ድምብላል፣ ኮሰረት፣ ስኳር ድንች ...ምናምን ይሸጣሉ። ብዙ ደንበኛ ያላቸው አይመስለኝም። ስንወጣ ስንገባ የደራ ገበያ አንድም ቀን አይቼ አላውቅም ።

ኔግሮ የትምርት ቤት ስሙ መቆያ ነው። እኛ ነን ኔግሮ የምንለው።

እኛ ትምህርት ቤት የሚማሩ የሰፈሩ ልጆች ሲጠሩት ሰምተን መሰለኝ መቆያን ትተን ኔግሮ የምንለው።

መቆያ የሚባለው ክላስ ስም ሲጠራ ብቻ ነው። ኔግሮ ሲባል ነው እሱም ደስ የሚለው።

የሆነ ቀን ሃይሚ ግርማ መፅሃፍ ጠፍቶብኝ ኔግሮ ሰጠኝ አለችኝ። ጠየኩት "ከራሷ ቦክመህ ለራሷ ገጫሃት ኣ?" ስለው ፤ ሲስቅ የሚያወጣትን ቀጭን ድምፅ አውጥቶ ሳቀ "ባክህ እኔ እንደኔ ችስታ እናት ካለው ቤተሰብ አልሰርቅም "አለ ።

ከስምንት ወደ ዘጠኝ ስንዘዋወር ኔግሮ ታስሯል አሉን። ስሰማ "ዕድሜው ለእስር ደርሷል ወይ?" ብዬ ያኔ አልጠየኩም።

የመንግስት ትምህርት ቤት ስለተማርን ለብዙ ነገር ከዕድሜያችን በላይ ነበርን። የሚታሰሩት በግሩፕ የሚጣሉ ልጆች ስለነበሩ ብዙ አልገረመኝም።

መስከረም አስራ ሰባት ቀን ኔግሮ ሞተ አሉን። እናቱን ስናያቸው ጥቁር ለብሰዋል፥ ጉስቁልናው ብሶባቸዋል። ጉሊት የደረደሩት ከዚህ ቀደም ለመሸጥ ከሚደረድሩት በዐይነትም በመጠንም ቀንሶ አየሁ ።

ሞትን ያኔ ነበር በቅርብ ያወኩት ....በቅርብ የማውቀው፣ ሲያወራ የሰማሁት፣ አብሬው የተጫወትኩት ጓደኛዬ ሞተ ሲባል። ያኔ ነው ለመጀመሪያ ግዜ ያመንኩት።

የታሰሩበት ክፍል የነበረው ካቦ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ፖሊስ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ታሞ ነው ይላሉ ....
ኔግሮ ሞተ። እውነት ነበር!

"ልጅ ይሞታል እንዴ?!" አልኩኝ
ለምን መቆያ አሉት ግን እናቱ??
በዛ ዕድሜው እንዴት በዛ ልክ አሰበላቸው??
በምን ይሆን የሚፅናኑት??
ለምን ሌባ ሆኖ ለጓደኞቹ ታመነ??

እንዴት የሰረቀውን እንደትልቅ ሰው አስቦ ተከራክሮ ሸጠ?? ላለፋበት ነገር እንዴት ዋጋ ሰጠ?? ለምን ምንም ከሌላቸው ሰዎች አልሰርቅም አለ??

በዛ ዕድሜው እንዴት አረጀ ?
እሺ ይሁን መርህ እና ሌብነት እንዴት አብሮ ሄደለት!!

እኔንጃ ኔግሮ ግን ሞተ አሉ !!!
© Adhanom Mitiku

ከመጽሐፍት መንደር💠

13 Jan, 17:50


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አስራሁለት


አቶ ለሜቻ ተንሰቅስቀው እያለቀሱ ነው..፡፡የቤቱ ሰው ሁሉ በድንጋጤ ተሸብሯል…፡፡በፀሎት የምትገባበት ጠፍቷት አብራቸው እንባዋን እያረገፈች ነው፡፡፡ልጃቸው ፊራኦል ላጠፋው ጥፋት አባትዬው ይቅር እንዲሉት በጉልበቱ ተንበርክኮ እየለመናቸው ነው፡፡
‹‹ልጄ ይቅር የምልህ..እያንዳንዱን የገዘኸውን ዕቃ ወይ በየገዛበት መልሰህ ካልሆነም ለሌላ በመሸጥ ገንዘቡን አንድም ሳታጎድል ለልጅቷ ስትመልስ ነው፡፡››
‹‹እሺ አባዬ እንዳልክ አደርጋለው፡፡››
‹‹እኮ ተነስና አድርግ››
‹‹አሁን እኮ መሽቷል….ነገ በጥዋት ተነስቼ እንዳልከው አደርጋለው››
‹‹እስከዛው ላይህ አልፈልግም፣ወይ ቤቱን ለቀህ ውጣ ወይ እኔ ልልቀቅልህ››
‹‹አረ አባዬ… አንተ ምን በወጣህ እኔ ወጣለሁ….››ብሎ ከተቀመጠበት ሲነሳ በፀሎት ከተቀመጠችበት ሆና ጣልቃ ገባች…ጋሼ የሆነው ነገር ሁሉ የእኔ ሀሳብ ነው….ቆርቆሮውም..ሲሚንቶውም ሁሉም የተገዛው በእኔ ሀሳብ ነው፡፡በወቅቱ እሱ እንደማይሆን ነገሮኝ ተቃውሞኝ ነበር..እኔ ነኝ ያስገደድኩት…ስለዚህ ወቀሳውም ቅጣቱም የሚገባው ለእኔ ነው…ለሊሴ ታክሲ ልትጠሪልኝ ትችያለሽ?››
ጥያቄዋ ሁሉንም ሰው አስደነገጠ፡፡
‹‹እንዴ ታክሲ ምን ሊያደርግልሽ?››ለሊሴ ጠየቀች፡፡
‹‹የጋሼን ቅጣት ተግባራዊ ለማድረግ ነዋ…ሆቴል ድረስ የሚወስደኝ ታክሲ ጥሪልኝ…ከቤት መባረር ያለብኝ እኔ ነኝ››
‹‹ተይ እንጂ ልጄ..ለምን ጡር ውስጥ ታስገቢኛለሽ?››አቶ ለሜቻ ለዘብ ብለው ተናገሩ
‹‹ጋሼ ..ይሄ ምንም ጡር አይደለም…ይሄንን እቃ ያስገዛሁት ለራሴ ስል ነው….ያው እንደምታዩት በዚህ አያያዜ ለመዳን ሁለትና ሶስት ወር ይፈጅብኛል ..ከዳንኩ በኃላም ቶሎ የምሄድበት ቦታ ስለሌለኝ ከእናንተ ጋር ቢያንስ ስድስት ወር ኖራለው..ስድስት ወር ሙሉ ደግሞ እንዲህ የለሊሴን መኝታ አስለቅቄ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ መኖር ከባድ ስለሆነ ነው

ሀሳብን ያመጣሁት..እኔ እንደውም ቤቱን ተረባርበን በአንድ ወር ውስጥ አልቆ እኔ ከእነለሊሴ ጋር እኖርበታለው ብዬ ነው››ስትል አብራራች፡፡
‹‹ልጄ ቢሆንም አግባብ አይለም..በእኛ ላይ ይሄን ሁሉ ብር መከስከስ እኛም አሜን ብለን መቀበል ነውር ነው…ሰውን ተይው …እግዚያብሄሩስ ምን ይለናል?››
‹‹አሁን ልጅህ ለሊሴ ብር አግኝታ እንዲህ ብታደርግ ይሄን ያህል ትበሳጭባታለህ?›› ዝም አሉ
‹‹ገባኝ አትበሳጭባትም….እኔንም እንደልጅህ አድርገህ ከምር ብትቀበለኝ ኖሮ ይሄን ያህል ቅር አትሰኝም ነበር..በቃ ለሊሴ ደውለሽ ታክሲውን ጥሪልኝ››
ለሊሴ  ፈራ  ተባ  እለች…  ስልኳን  ከተቀመጠበት  አነሳችና  ለመደወል  ስትዘጋጅ  ጋሽ ለሜቻ‹‹ልጄ ስልኩን አስቀምጪው..እስኪ ሁላችሁም ተቀመጡና እንረጋጋ…››
‹‹አዎ  ልጆች  ሁላችሁም  ተቀምጡ….ለሊሴ  እስኪ  ሲኒውን  አቀራርቢና  ብና እናፍላ››እናትዬው ውጥረቱ ረገብ ስላለ ተደስተው የተናገሩት ነበር፡፡
////
በማግስቱ

‹‹…አየሩ በጥላቻ ጥላሼት ጠቁሯል፡፡ከፍቅር ዕጦት በሚመጣ የፍራቻ ግንብ ተከልያለው….በንዴቴ አጥር ስር ተሸሽጌ እየተንቀጠቀጥኩ ነው፡፡ይበርደኛል..አዎ በጠራራ ፀሀይ ይበርደኛል…ይርበኛል..እየበላው ሁሉ ይረበኛል….፡፡ጉሮሮዬ በጥማት ተሰነጣጥቆል….ግን ከዛ ከጥማቴ የሚፈውሰኝ ውሀም ሆነ ምድራዊ ወይን የለም፡፡››በፀሎት ነች የምታወራው…ፊራኦል ግን ምንም አልገባውም
‹‹አንዳንዴ እንደፈላስፋ ነው የምታወሪው?››
‹‹እንደእኔ ህይወትህን ሙሉ በብቸኝነት በራፍ ዘግተህ ለብዙ ሰዓታት በትካዜና በቁዘማ የምታሳልፍ ከሆነ ወደፈላስፋነት መቀየርህ የግድ ነው፡፡ከሞት ደጃፍ ደርሶ..በቃ አበቃልኝ ብሎ ተስፋ ከቆረጠ በኃላ ወደህይወት ተመልሶ ሁለተኛ እድል የተሰጠው እደእኔ አይነት ሰው ነገሮችን በተለየ መልክ ባያይ ነው የሚገርመው፡፡›››

‹‹አልገባኝም የሞት አፋፍ ላይ መድረስ ስትይ?››
ደነገጠች..አንደበቷን አንሸራቷት ሚስጥር ልታወጣ በመድረሶ እራሷን ወቀሰችና‹‹ማለቴ በዛ ለሊት በሞተሬ ከእዚህ በራፍ ጋር ስለ መጋጨቴ እያወራው ነው…የሞትኩ ማስሎኝ ነበር እኮ››
‹‹እ..እሱ እንኳን እውነትሽን ነው….ግን አሁን ፊትሽ ቁስሉ ደርቆል እኮ …ለምን ቀንና ለሊት በሻርፕ ትሸፍኚዋለሽ…››
‹‹እርግጥ እንዳልከው ድኗል ግን ጠባሳው ያስጠላል..እንዲህ ሆኜ ሰው እንዲያየኝ አልፈልግም ..በተለይ ወንዶች ››
ፈገግ አለ….‹‹ዝም ብለሽ እያካበድሽው ነው እንጂ እርግጠኛ ነኝ ከነጠባሳሽ በጣም ቆንጆ ልጅ ነሽ…እንደውም እንዲሁ አቋምሽን ሳየው የት እንደሆነ የማውቃት አርቲስት ወይም ሞዴል ነገር እየመሰልሽኝ ደነግጣለው፡፡››
‹‹አየህ አንደውም ለዚህ ነው ፊቴን ዘወትር በሻርፕ ምጆብነው››
‹‹አልገባኝም››
‹‹ሙሉ በሙሉ ገልጬልህ ፊቴን በደንብ ካየኸው የትኛዋ ሞዴል ወይ አርቲስት እንደሆንኩ ወዲያው ስለምትለየኝ፣እንደዛ እንዳይሆን ስለፈለኩ ነው››
‹‹ትቀልጂያለሽ አይደል?››
‹‹ምን ላድርግ ብለህ ነው….በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ውስጥ ያለ እንደእኔ አይነት ሰው ባይቀልድ ነው የሚገርመው››
‹‹እስኪ እርእሱን እንቀይር ፣ሌላው ስለአንቺ የሚገርመኝ  እስከአሁን ሞባይል ይዘሽ አለማየቴ ነው››
‹‹የለኝም…..ማለቴ ከቤቴ ስወጣ ይዤ መውጣት አልቻልኩም፡፡››
‹‹ታዲያ  ልግዛልሽ…ማለቴ  በራስሽው  ብር  የምትፈልጊውን  አይነት  ስልክ  ልገዛልሽ እችላለሁ፡፡››

ፈገግ አለችና‹‹በራስህ ብር ብትገዛልኝ አይሻልም?››
‹‹ደስ ይለኝ ነበር..ግን አቅሜ ላንቺ የሚመጥን ስልክ ለመግዛት በቂ አይመስለኝም…››
‹‹የእኔ አቅም ምን ያህል ነው..?በምንስ ሚዛን ለካሀው…?ለማንኛውም ለጊዜው አያስፈልገኝም…ስፈልግ ግን ነግርሀለው፡፡››
‹‹ይገርማል… በአንቺ እድሜ ያለች ሴት ስልክ አያስፈልገኝም ስትል አጃኢብ ነው፡፡››
‹‹ምኑ ይገርማል..?ለጊዜው ማንም ጋር ለመደወል እቅድ የለኝም..››
‹‹ሶሻል ሚዲያስ….እንዴት ያስችልሻል፡፡››
‹‹ዕድሜዬን ሙሉ ስልክና ላፕቶፕ ላይ አረ አንቺ ልጅ አይንሽ ይጠፋል እየተባልኩ እስክሪን ላይ አፍጥቼ ነው የኖርኩት…ሶሻል ሚዲያ ከጨለማ ሀሳቦቼ እና ከድብርቶቼ መሸሺጊያ እና መደበቂያ ዋሻዬ  ነበር…አሁን  ግን ችግሮቼን ፊት ለፊት መጋፈጥ  ነው የምፈልገው
….እስከአሁን ከኖሩኩት ህይወት በተቃራኒ ነው መኖር የምፈልገው፡፡ይልቅ ከቻልክ ነገ መፅሀፎች ገዝተህልኝ ትመጣለህ፡፡››
‹‹እሺ ምን ምን መፅሀፍ እንደምትፈልጊ ትንግሪኝና ገዝቼልሽ መጣለው፡፡››
‹‹ጥሩ አሁን ደግሞ ምርጥ አንድ ሙዚቃ ብትጋብዘኝ በጣም ደስተኛ እሆናለው…››
‹‹ጥሩ …አለና ከአጠገቡ ያለውን ክራር አንስቶ ክሮቹን በእጁ እያጠበቀ እና እያላላ ቅኝቱን አስተካከለና‹‹ምን አይነት ዘፈን ይሁንልሽ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹መቼስ በዚህ ውድቅት ለሊት ስለሀገር ዝፈንልኝ አልልህም…የፍቅር ዘፈን ይሁንልኝ፡፡›› እንደማሰብ አለና ክራሩን መገዝገዝ ጀመረ ..አፏን ከፍታ ነበር የምታዳምጠው…
የነገን ማወቅ ፈለኩኝ … መጪውን አሁን ናፈቅኩኝ.. የፍቅር ምርጫዬ አንቺ ነሽ…ልቤንም መንፈሴን የገዛሽ ወሰንኩኝ ልረታ አስቤ፣አካሌን መንፈሴን ሰብስቤ

ከመጽሐፍት መንደር💠

13 Jan, 17:06


ፈላጊህ መብዛቱ ኪስህ በሞላ እለት፣
ጓደኛህ መክፋቱ ኪስህ በሳሳ እለት።
ስታጣ ሚሄደዉ ስታገኝ ይመጣል፣
ብር አምላኪ በዝቶ #ፍቅርም ለካ ጠፍቷል።

ከመጽሐፍት መንደር💠

12 Jan, 17:37


Behailu Mulugeta እንደጣፉት
ይህ መርፌ..
ልጄን ለማውጣት ሲባል በሚስቴ ጀርባ የገባ #ይህ_መርፌ!
.
.
ነርቯን ለማግኘት ሲባል የጀርባዋ ማለቂያ ላይ ተሰካ። ግማሸ ሰውነቷ በደነላቸው። ቁልቁል እንዳታይ ከአንገቷ በታች መጋረጃ ተዘርግቷል!
.
ቀዶ ጥገናውን ተጀመረ። "አህ" አለች።
"እንዴ! ትቅሚያለሸንዴ?" አሏት።
ፈርታለች እንጂ የኔ ሚስት
"የታለ? ወይም መቼ?" ነበረ የምትለው😁
.
በአፏ በኩል ደገሟት። እኔ ውጪ ዳዊት ደግማለሁ።
.
relax እንድታደርግ መዝሙር ከፈቱላት። "ቅኔ ከአፌ ፈሰሰ" ይላል። የምትወደው መዝሙር። በሰመመን ሆና መዘመር ገባች!
እጇ ታሰሯል እንጂ አታሸበሽብም ብላችሁ ነው😁
.
ዶክተሮች በሁኔታዋ ፈገግ ማለታቸው አልቀረም።
.
አካሏ ከቀዶ ጥገና ክፍል እየተገፋ ወጣ። አንሶላ ብቻ ጣል ተደርጎባታል። ብቻዬን የማየው ይሔ ገላ ኮሪደር ለኮሪደር እንደ ስጋ ተገፋ። ከአይን እና ጥቂት የአንገት እንቅስቃሴ በስተቀር ሚስቴ የለችም። በአንሶላ ወጥረን አነሳናት። ባል ነኝና አስደበረኝ ይሔም። ባል "በኔ ብቻ የመጣ አይደለም" እያለ ልቡን ይደግፍ።
.
እያሾፍኩ መሆኑ የገባኝ ቆይቶ ነው።
.
ከተቀደደችበት ቦታ ይልቅ አድባ እንድትቀደድ የረዳት ያ መርፌ ለካ አሻራው ቀላል አይደለም። ቁስሉ ደርቆ ተንቀሳቀሽ ሲሏት የስለት ዣንጥላ ይመስል ታጥፋ ተነሳች። ሚስቴም እንደ ልጄ አንገቷን በራሷ መደገፍ የተሳናት ሆነች።
.
የማስታገሻ አይነት ዋጠች ማስታገሻው ያደረሰውን ጉዳት ልታስታግስ። ራስምታቱ ደሞ ሌላ ነው። በዛ ላይ ደሙ እንዲወርድ እያሉ ሆዷን እንደምለዋ ያሹታል። ቆጣ ያለ ዶክተር መጥቶ "ተነስተሽ ወክ አድርጊ" ይላል።
.
ጌታሆይ!🥺
እኔስ ግዜ ምን እያደረግኩ ነው?...
ከየአቅጣጫው #እንኳን_ደስ_አለህ እየወረደብኝ። "ታድለህ ሴትናትንዴ" ታድለህ እየተባልኩ።
.
አሁን እኔም ወላጅ ነኝ አ? ወንድ አስወላጅ እንጂ ወላጅ ሊባል አይገባውም አልኩ ግራ ቀኙን ሳልገላመጥ። ለደስታዬ በረጨሁት እሷ ዘጠኝ ወር ቋቅ አላት። ወልዳም አታርፍ።
.
አዳም የሔዋን ባል በለስ ስላበላችው "አሳች" ብሏት ነበረ። ልጅ ስትወልድስ? #ሒወቴ_ነሽ አላት። #የህያዋን_ሁሉ_እናት_ነሽ ሲል ሔዋን አለ።
.
እንደ አዳም ሰራኝ። ለሰርጋችን እህቶቿ ፊት ፎቶ አንሺው ሳም ሲለኝ ያፈርኩ ሰውዬ እናቷ ፊት አይዞሽ እያልኩ ሳምኳት።
.
ለዘጠኝ ወር በጀርባና በሆዷ መተኛት ሲያምራት እየተገላበጥኩ ተኝቻለሁ ጎኗ። "ኧረ በቀኝ ጥሩ አይደለም" ሲሏት ጎድኗ እስኪያብጥ በአንድ በኩል ተሰየፈች። ከወለደች በሗላ ደሞ በግራና ቀኝ አይቻልም በጀርባሽ ያለትራስ ብለዋታል🥺
.
ሴት በመውለድ ትድናለች እንዲል ይህ መድሀኒት ይሁንልሸ!
.
የወለዳችሁ ሴቶች ለናንተ ትልቅ ክብር አለኝ🙏

ከመጽሐፍት መንደር💠

03 Jan, 03:14


ከረጅም ግዜ በኃላ ፍሬንዴን አገኘሁት። ፈታ ያለ ነው። ሳቅ ያበዛል ሰላምታ ሲሰጥ እቅፍ አደርጎ ነው።

ያቆላምጣል ...

ሲስቅ አይኑ፥ ጥርሱ፥ ጉንጩ ቅይር ይላል። እሱን ማግኘት Energy ይሰጣል ።

ከዓመት በኋላ ሳገኘው '...ባክህ ፋዘርም ብራዘርም ደየሙብኝ.. በተከታታይ...' አለ።...ትክ ብዬ...በመደናገጥ አየሁት።

'ቤትም ሱቅም ወረስኩ ... በልጅነቴ ኪራይ ሰብሳቢ ሆንኩልህ...' ብሎ ሌላ ሳቅ ለቀቀ።

እንዳንድ ሰው ቀለል የሚያደርገው ነገር አገራረሙ ..

ሌላ ቀን ሌላ ቦታ እየሄድን...

"የሞተ ሰው በአይንህ አይተህ ታውቃለህ?" አልኩት።

'አባቴ ድንገት ታሞ ተሯሩጠን ከወንድሜ ጋ ሆስፒታል ወሰድነው አልቆየም ነርሷ ሞተ አለቺኝ እንዲ አትበይ ተይ ተይ ተይ አልኳት...
ያልነገርኩት ነገር አለ ተይ አልኳት...ተይ ደስ የሚለውን በልደቴ ቀን እነግረዋለሁ ብዬ ያቆየሁት ነገር አለ ተይ ሞተ አትበይ አልኳት...'

ያለቺው ነበር የሆነው።

'እኔና ከወንድሜ ከነርሷ ጋር በጋራ ሆነን ገነዝነው።'

'እምባ እየከለለኝ እጄ አልታዘዝ እያለ እኔ ነኝ ለቀብር ያበጃጀሁት...

ልጨምርልህ...?!

ፈገግታው በእንባ ተቀይሯል፤ ድምፁ ሳግ አለው፤ ዐይኑ እምባ ተሞልቷል...

'አባቴ በሞተ በሰባት ወር ወንድሜ እጄ ላይ ነው የምተው። ወደቀ ተብዬ ስጠራ ስበር ደረስኩ ያኔ ነብሱ አልወጣችም ነበር እንዳቀፍኩት፥ እየጠራሁት፥ አይዞህ እያልኩት፥ ውኃ አምጡ ላፍስስለት እያልኩ እጄ ላይ ሞተ...።'

ከእማማ እልፍኝ ጋ ሆኜ ገነዝኩት...

'ታላቄን የሚቆረቆርልኝን ገነዝኩት። ዐይኑ፥ ገላው፥ በድን ሲሆን አየሁ ...አብሮ አደጌን አንድ ወንድሜን ቀበርኩት...'

'ከዓለም ተኳረፍኩ። ጠዋት ማታ ዊድ ነፋሁ፤ ወንድሜ አግብቼ እኖርበታለሁ ያለው ቤት፤ አባቴ የሚጦርበት ሱቅ የኔ ሆነ። መጠጥ ውስጥ ተደበኩኝ በዊድ ተከለልኩ።

'ስጋችን እንዴት እንዳስጠላኝ፤ ሰውነት እንዴት እንደደበረኝ፤ ነገ እንዴት እንደቀፈፈኝ፤ ዕቅዴን እንዴት እንደናኩት!!'
.
.
ሳቃችን የከለለው ሃዘን ብዛት !!!

©Adhanom Mitiku

ከመጽሐፍት መንደር💠

02 Jan, 18:41


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ዘጠኝ
አቶ ኃይለ መለኮት እቤታቸው ባለ የገዛ ቢሯቸው ውስጥ ተሸከርካሪ ወንበራቸው ላይ ተቀምጠዋል…በቀኝ እጃቸው የሚያብረቀርቅ ማካሮብ ሽጉጣቸውን ይዘው ፊታለፊታቸው ያሉት ሶስት ግለሰቦች ላይ በየተራ እያነጣጠሩ ምላጩን በስሱ እየዳበሱ ይናገራሉ
‹‹በመጀመሪያ ማንን ልግደል?››
‹‹ጌታዬ ይቅር ይበሉን…አጥፍተናል….››

‹‹አጥፍተናል….ጥፋት እኮ በቀላሉ ሊስተካከል የሚችል ስህተት የሆነ ድርጊት ስታደርግ ነው፡፡ለምሳሌ እዚህ መኖሪያ ቤቴ ላይ ጋዝ አርከፍክፈህ ክብሪት በመለኮስ ግማሹን ህንፃ ብታወድመው ጥፋት አጥፍተሀል ብዬ የጠየቅከውን ይቅርታ ልቀበልህ እችላለው፡፡ ምክንያቱም እቤቱን አሁን ካለበት ይዘት ይበልጥ አስውቤ ከእንደገና ላስገነባው እችላለሁ…ወይም ከፋብሪካዎቼ ትልቁን መርጠህ ሙሉ በሙሉ ብታወድመው እንደጥፋት ቆጥሬ ይቅርታህን ልቀበል እችላለው…ወይንም ሽጉጥህ ባርቆብህ ቀኝ እጄን ብትመታኝና በዛ የተነሳ እጄ ቢቆረጥ አዎ ይቅርታህን ልቀበል እችላለው፡፡ግን አሁን ምንም አላስቀረህልኝም፡፡ልጄ ሁለ ነገሬ ነች…ምንም መተኪያ ምንም ማካካሻ የላትም…ያ ማለት ይቅርታ ላደርግላችሁ ፈፅሞ አልችልም.››
‹‹ጌታዬ ይገባናል፣ አንተ ትክክል ነህ..ግን ቢያንስ በፍለጋው ላይ ጠንክረን እየሰራን ነው….የሆነ ትንሽ ቀን ጨምርልንና አቅማችንን አሟጠን እንፈልጋት… የሆነ ያህል ጊዜ ስጠን… ካልተሳካልን ያሰብከኸውን ታደርጋለህ፡፡››
‹‹አዎ እሱማ አደርጋለው….ዋጋማ ትከፍላላችሁ….አሁን የምናደርገው…..››ንግግራቸውን ሳያጠናቅቁ ስልካቸው ጠራ…የደቀኑትን ሽጉጥ ሳያወርድ ስልኩን አንስተው ማውራት ጀመሩ፡፡
‹‹እሺ…ጥሩ …ሶስቱም ነው እይደል… በጥንቃቄ ጠብቋቸው››
ስልኩን ከዘጉ በኃላ ንግግራቸውን ቀጠሉ‹‹ስልኩ ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ…?የእናንተ የሁለታችሁን አንዳንድ ልጃችሁን ያንተን ደግሞ ምትወዳትን ሚስትህን አሳግቼቸዋለው…ልጄ በሚቀጥሉት ሶስት ቀን ውስጥ ተገኝታ ወደቤቷ ካልተመለሰች ያው የምወዳትን ልጄን ስላሳጣችሁኝ ለዛ ክፍያ የምትወዱትን ሰው ታጣላችሁ ማለት ነው፡፡››ሲል ሰቅጣጭ መርዶ አረዷቸው፡፡
ሶስቱም ሰዎች ላይ የታየው ድንጋጤ ሲኦላዊ ነበር፡፡፡አቶ ኃይለልኡል ሰዎቹን ከቢሮቸው አሰናብተው ሽጉጡን ወደመሳቢያው ውስጥ መልሰው በማስቀመጥ ቆለፉበትና ወጥታው ወደ ባለቤታቸው ወ.ሮ ስንዱ መኝታ ቤት ሄዱ ….ሚስታቸው አልጋው ላይ ተሰትረው ጉልኮስ ክንዳቸው ላይ ተሰክቶ እህህ እያሉ ነው..ለዘመናት ወደዋቸው የማያውቁት ባላቸውን ድምፅ ሲሰሙ የከደኑትን አይን ገለጡ እና በመከራም ቢሆን ከንፈራቸውን አነቃነቀው ማውራት ጀመሩ

‹‹ኃይሌ…ልጃችን አልተገኘችም?››
‹‹አይዞሽ አታስቢ ..ትገኛለች….አንቺ ምንም አትጨነቂ››ሊያፅናኗቸው ሞከሩ፡፡
‹‹እንዴት አልጨነቅ…?በዚህ አለም ላይ ያለቺኝ እሷ ብቻ ነች..በህይወቴ ሙሉ የበደልከኝን በደል እንድረሳልህ…የሰራህብኝን ስራ ይቅር እንድልህ ከፈለክ ልጄን አግኝልኝ….ልጄን ካገኘህልኝ ያልከኸውን ሁሉ አደርግልሀለው….እንደውም ምንም ሀብት ሳልካፈልህ እፈታሀለው…እፈታህና ገዳም እገባለው..አዎ ልጄ ሰላም መሆኗን ካረጋገጥኩ ከህይወትህ ዞር እልልሀለው››
‹‹አረ ተይ …ለእኔም ልጄ እኮ ነች…እሷን ለማግኘትና ወደቤቷ ለመመለስ ከአንቺ ጋር ይሄንን አድርጊልኝ እያልኩ የምደራደር ጭራቅ ነገር እመስልሻለው….?ተይ እንጂ..አሁን ወጣ ብዬ ፖሊሶቹ ምን ላይ እንደደረሱ መጠየቅ አለብኝ..ሀኪሞቹ ሚሉሽን ስሚና ጤናሽን ተነክባከቢ..ልጃችን ስትመጣ እንደዚህ ሆነሽ እንደታገኚሽ አልፈልግም…እናቴ በእኔ ምክንያት ሽባ ሆነች ብለ መፀፀት የለባትም››ብሎ ወጥቶ ሄደ…..
///
በፀሎት ከእንቅልፏ የባነነችው በቤቱ ውስጥ ግርግር እና የብዙ ሰው ድምፅ ስትሰማ ነበር..አይኖቾን ስትገልጥ ግን ያሰበችውን ያህል ብዙ ሰው አልነበረም ነበር…ወ.ሮ እልፌ
፤አቶ ለሜቻና አንድ ሙሉ ሱፍ የለበሰ ጎልማሳ ሰው ነበር በቤቱ ያሉት….ግን ያ ጎልማሳ ሰው ሲያወራ ድምጹ መመጠኛው እንደተበላሸበት ማይክራፎን ከጣሪያ በላይ ይጮኸ ስለነበረ የብዙ ሰው ድምጽ ይመስላል….
አይኗን ስትገልጥ አየና ወደእሷ ተጠጋ.‹‹ልጄ ተነሳሽ..?ጥሩ …ይሄ ዶክተር ታፈሰ ይባላል..የጓደኛዬ ልጅ ነው….አንቺን እንዲያይልኝ አስቸግሬው ነው፡፡›››አቶ ለሜቻ ናቸው ተናጋሪው፡፡
‹‹አባቴ ዝም ብለህ ነው እኮ የተቸገርከው..ደህና ነኝ እኮ››
ከወ.ሮ እልፍነሽ ጋር በተስማማችው መሰረት ቢሻክራትም አንቱታውን በአንተ ቀይራ ማውራት ጀመረች…
‹‹ደህና መሆንሽና አለመሆንሽን እኔ ሀኪሙ አይቼ ብወስን አይሻልም›› ዝም አለችው….
ወደእሷ ተጠጋና  አያት…ግንባሯና ከፊል ፊቷ በስነስርአት መታሸጉን አረጋገጠና  ..አንድ መርፌ በክንዷ ወግቷት መድሀኒት አዘዘላት…
‹‹በቃ ጋሼ..የወንድሞት ልጅ በጥሩ ሁኔታ ላይ ትገኛለች..ቁስሉ ጊዜውን ጠብቆ ፋሻው ተነስቶ በደንብ ፀድቶ ከእንደገና መታሸግ አለበት…›››
‹‹ምንም የሚያሰጋ ነገር የለም እያልከኝ ነው?››
‹‹አይ የለም ሰላም ትሆናለች..ግን ምን አልባት ፊቷ ላይ ጠባሳ ሊሆንባት ይችላል፡፡››
‹‹ያንን ማስቀረት አይቻልም?››አቶ ለሜቻ ጠየቁ፡፡
‹‹ያው የቆዳ ስፔሻሊስቶች ያስተካከሉታል..በአሁኑ ጊዜ ብር ካለ የማይስተካከል ነገር የለም..ዋናው በህይወት መትረፏና አካለ ጎዶሎ አለመሆኗ ነው…የጠባሳው ነገር የገንዘብ ጉዳይ ነው… ይስተካከላል፡፡››
‹‹ይሁን እንግዲህ…….አንተንም አስቸገርኩህ››
‹‹አረ ጋሼ…ለርሶ ባልታዘዝ አባቴ አያናግረኝም….በማንኛውም ሰዓት ካመማት ደውሉልኝ..አሁን ልሂድ….፡፡እግዜር ይማርሽ እህቴ››
‹‹አመሰግናለው ዶ/ር፡፡››
‹‹ዶ/ር አቶ ለሜቻን አስከትሎ ቤቱን ለቆ ወጣ ..ክፍል ውስጥ ወ.ሮ.እልፍነሽና በፀሎት ብቻ ቀሩ፡፡
‹‹ጋሼ ዝም ብሎ እኮ ነው የሚጨነቀው?››
‹‹እሱ..እንዲሁ ነው….ታያለሽ ነገ ደግሞ ሌላ ዶክተር ለምኖ ይዞ ይመጣል..እስክትድኚ እረፍት አይኖረውም››
አቶ ለሜቻ ተመልሰው ከመምጣታቸው በፊት ለሊሴ ከሄደችበት ተመልሳ መጣች፡፡ ይዛ የመጣችው ዕቃ ግን የሳሎኑን ግማሽ የሸፈነ ነበር….ከአምስት በላይ ፔስታል ከባለታክሲው ጋር እየተጋገዙ ወደውስጥ አስገቡ….ከገዛችው ዕቃዎች ውስጥ ለበፀሎት አዲስ አንሶላዎች
…ምቾት ያለው ብርድልብስ ፣ቢጃማ ..ሸበጥ ጫማ..ቅባት…ፓንቶች..ብቻ ያስፈልጋታል ያለችውን እና በእይታዋ የገባላትን ዕቃ ሁሉ ገዝታ ነበር..ከዛ የቤት አስቤዛ አትክልቱን..ፍራፍሬውን..ፓስታ ..መኮሮኒ..ስጋና የመሳሰሉትን እልክ የታጋባች ይመስል ቤቱን ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በቁሳቁስ ሞላችው…፡፡
አቶ  ለሜቻ  ዶክተሩን  ሸኝተው  ሲመለሱ  ትተው  የሄዱት  ሳሎን  ሌላ  መልክ  ይዞ ሲጠብቃቸው ከመደንገጣችው ብዛት ባሉበት ደርቀው ቆሙ….
‹‹ሊሊሴ ምንድነው ይሄ ሁሉ?››
‹‹አየህ አባዬ አንሶላው አያምርም… ብርድ.ልብሱስ….?.የሄው ቢጃማም ገዛሁላት…››
‹‹ጥሩ አደረግሽ…ብሩን ከየት አመጣሽው?››
‹‹እኔማ ከየት አመጣለው….እራሶ ሰጥታኝ ነው፡››አለች ወደበፀሎት እየጠቆመች፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

30 Dec, 18:50


‹‹ያው የተገኘውን ነዋ….ከሁለት አመት በፊት ነው ከተግባረእድ በፀጉር ስራ የተመረቀችው…..አፈሩን ገለባ ያድርግላትና ሁለት አመት ከፍላ ያስተማረቻት ሟች እህቷ ነበረች…የሆነ ቤት ተቀጥራ ለአንድ አመት ሰርታ ነበር ፡፡አልተስማማችም መሰለኝ ሰሞኑን ለቀቀች ….አሁን ሌላ ቦታ እየፈለገች ነው፡፡ አንድ ወዳጇ ፀሀፊነት አግኝቼልሻለው ብላት ያንን ለማረጋገጥ ነው የሄደችው፡፡››
የሞቿ ስም ሲጠራ እንደተለመደው የበፀሎት ሰውነት ሽምቅቅ አለ‹‹ግን እቤታችሁ ፊት ለፊት ነው….የሆነች ትንሽ ክፍል ቢኖር እኮ የራሷን ስራ ብትሰራ ጥሩ ነበር››

‹‹እሱማ እንዳልሽው ጥሩ ነበር …ልጄ ግን ቀላል ይመስልሻል…?ለእኛ ያንን ማድረግ ከባድ ነው፡፡እህቷ ልክ አሁን አንቺ እንዳልሺው አይነት እቅድ ነበራት…ተምረሽ ስትጨርሺ ከምሰራበት ባንክ ተበድሬም ቢሆን የራስሽን ፀጉር ቤት ከፍትልሸለሁ ብላ ቃል ገብታላት ነበር…ልጄ ቃሏን የምታጥፍ ሰው አልነበረችም……››እንባቸው በአይናቸው ግጥም ብሎ ረገፈ….አብራ አለቀሰች…እንደምንም ለመረጋጋት እየሞከሩ ንግግራቸውን ካቆሙበት ቀጠሉ‹‹እንዳልሺው…እንደምንም እቤቱን ብንሰራላት እንኳን ማሽኑን ከየት መጥቶ ይገዛል…..እንዳልሽው ግን አንድ ቀን እንደዛ ማድረጋችን አይቀርም…››በትካዜ መለሱላት፡፡
‹‹እማዬ››
‹‹አቤት ልጄ››
‹‹የሆነ ቦርሳ ነበረኝ አይደል..?››
‹‹አዎ አለሽ ..ላምጣልሽ?››
‹‹አዎ ካላስቸገርኮት››
‹‹የምን መቸገር አመጣሽብኝ..አመጣልሻለሁ››አሉና የበላችበትን እቃ ከተቀመጠበት አንስተው ወደውስጥ በመግባት ከደቂቃዎች በኃላ ቦርሳውን አንጠልጥለው አመጡና ስሯ አስጠግተው አስቀመጡላት፡፡
ዚፑን ከፈተችና ከላይ ያሉትን ሁለት ጅንስ ሱሪ…ሁለት ቲሸርቶች አወጣችና አልጋ ላይ አስቀመጠች….ከዛ በኃላ ያለውን እስር እስር ባለሁለት መቶ ኖት ብር ነው…ስንት ብር እንደሆነ አታውቅም …በተለያየ ጊዜ ዝም ብላ ቁም ሳጥኗ ውስጥ እየወረወረች ያጠራቀመችው ገንዘብ ነው..ምን አልባ ሶስት ወይም አራት መቶ ሺ ብር ይሆናል፡፡አንዱን እስር አወጣችና ልብሱን መልሳ ከታ.. ዚ..ፑን ዘጋችና ከራስጌዋ አስቀመጠችው…
‹‹እማዬ..››
አቀርቅረው ሲኒ እያጠቡ ነበረ ..ስትጠራቸው ቀና አሉና‹‹አቤት ልጄ.. ጠራሺኝ?››አሉ
‹‹እንኩ ይሄንን ብር››
ለደቂቃዎች ያህል ክው ብለው አዮት…‹‹ምን እያልሽ ነው ልጄ?››

‹‹ለቤት አንዳንድነገር ይግዙበት….››
‹‹እንዴ ይሄን ሁሉ ብር?››
‹‹ትንሽ እኮ ነው…ሀያ ሺ ብር ነች››
ፈገግ ብለው ‹‹አይ ልጄ… ሀያ ሺ ብር እኮ በአንድ ጊዜ እንዲህ ከነክብሩ እዚህ ቤት ገብቶ አያውቅም..በይ መልሺው…..ከህመምሽ ስታገግሚ ያስፈልግሻል፡፡››
‹‹አይ አያስፈልገኝም…››
‹‹አይ ልቀበልሽ አልችልም….ለሜቻስ ዝም ሚለኝ ይመስለሻል?››
ከጎኗ ያስቀመጠችውን ሻንጣ መልሳ ሳበችና ዚፕን እስከመጨረሻው በመክፈት.. ከነልብሱ ዘቅዛቃ ፍራሹ ላይ ዘረገፈችው….
ወ.ሮ እልፍነሽ በህልማቸው እንኳን አይተው የማያውቁት አይነት የብር ቁልል እየተመከቱ ነው..ያለፍቃዳቸው የተከፈተውን አፋቸውን መልሰው መክደን አቃታቸው፡፡
‹‹አዩ አይደለ….ይሄ ሁሉ ብር አለኝ….ደግሞ አዩት ይሄንን ሀብልና የጆሮ ጌጥ ብዙ መቶ ሺ ብር የሚያወጣ ነው..ከቸገረኝ እሸጠዋለው….እና ይሄንን ብር ይቀበሉኝና እቤት ውስጥ የጎደለውን ነገር ያሟሉበት….ደግሞ እናንተ ማለት እግዚያብሄር ለእኔ የሰጣችሁ ስጦታዎቼ ናችሁ …እንኳን ብሬን ህይወቴን እሰጣችኃላው፡፡የተገለበጥኩት መንገድ ላይ ወይም ሌላ ሰው ጊቢ ቢሆን አኮ…እንኳን ብሬን ህይወቴን እንኳን ማትረፍ አልችልም ነበር…እዛው ሳጣጥር ገድለው ቀብረውኝ ..ገንዘቡን በሙሉ ይወስዱት ነበር፡፡››
‹‹በስመአብ በይ ልጄ ….ተይ ተይ…››
‹‹እውነቴን ነው….እናንተ ሻንጣውን እንኳን ምን እንዳለበት ከፍታችሁ አላያችሁትም››
‹‹የሰው ዕቃ ያለፍቃድ እንዴት ይታያል …?.ነውር አይደለ እንዴ?››
‹‹እኮ እኔም ለማለት የፈለኩት ያንን ነው..በዚህ ዘመን ነውር የሚባል ነገር ጠፍቷል…ሰው ቁስአምላኪ ሆኗል….እምነት ..ሀቀኝነት ..ክብር  …እውነት ….የሚባሉ ቦዶ ቃላት ሆነዋል››
‹‹ካልሽ እሺ ልጄ……ለሜቻ ግን ምን ብዬ እንደማስረዳው አላውቅም››

‹‹ግድ የሏትም ጋሼን እኔ አሳምናቸዋለሁ፡፡››
ብሩን ተቀበሏትና..‹‹ልጄ እቤቴን እንዲህ እንደሞላሽው ላንቺም የሞላ ህይወት ይስጥሽ..››አይናቸውን ግድግዳው ላይ ወደተሰቀለው የሞች ልጃቸው ፎቶ ላኩና ፍዝዝ ብለው‹‹ልጄ  እንዲህ ድንገት መጥታ መአት ብር እጄ ላይ በማስቀመጥ ..እማዬ የሚያስፈልግሽን ነገር ግዢበት ..እቤት የጎደለ ነገር ካለ አሟይ…ትለኝ ነበር….አንድ ቀን የራሷን ኑሮ ሳትኖር እንደጓደኞቾ ጌጣጌጥና መዘነጥ ሳያምራት ቤተሰቦቾን እንዳገለገለች ሞተች….አሁን ሳስበው ልጅ ከጊዜዋ ቀድማ እንደዛ በስላ ትልቅ ሰው የሆነችውና በደግነትና ቤተሰቦቾን በማገልገል ብኩን የሆነችው ምን አልባት ቶሎ እንደምትሄድ አውቃ ይሆን እንዴ
?እላለሁ..ብቻ ተይው…..አንቺን እግዜር ይባርክሽ››
‹‹አሜን እማዬ››
‹‹ልጄ››
‹‹ወይ እማዬ››
‹‹እማዬ  ማለትሽ  ካልቀረ  …አንቱታውን  ተይው…ልጆቼ  አንቺ  ነው  የሚሉኝ
…..አባታቸውንም አንተ ነው የሚሉት…እንግዲህ አንቺም ልጃችን ሆነሽ የለ….ከአነሱ ለምን ትለያለሽ..አንቱታውን ተይው››
‹‹አመሰግናለው እማዬ…..በጣም ነው ማመሰግነው..አሁን ትንሽ ልተኛ፡፡››
‹‹ተኚ ልጄ.. ተኚ››አሉና ወደጓዲያቸው ገብተው…አሮጌ ሞባይላቸውን ፈለጉና ለልጃቸው ለለሊሴ ደወሉና ስራ ፍለጋውን ጥላ ወደቤት እንድትመጣ ነገሯት….
እንደመጣች ወደጓዲያ ወስደው ብሩን እያሳዩ የሆነውን ሲነግሯት ከመደንገጧ የተነሳ አፏ እንደኩበት ደረቀና ምላሶን ምታረጥብበት ምራቅ አጣች…ይህቺ ልጅ ለ በቤቱ መከራ ወይ መዘዝ አስከትላ ትመጣለች የሚል ከፍተኛ ፍራቻ በውስጦ ሲገላበጥ ነበር..ተቃውሞዋን እንደወንድሟ አውጥታ አታንጸባርቀው እንጂ በውስጧ ለመቶኛ ጊዜ ደጋግማ አስባበታለች…አሁን ግን እናቷ እየነገሯት ያሉት ተቃራኒውን ነው…መአት ሳይሆን በረከት ነው እጃቸው ላይ ያለው…በዛ ላይ ጥሩ ገድ አላት…ለወር ስራ ፍለጋ ስትኳትን ነበር..አሁን  ግን  የተሻለ  የተባለ  ስራ  ባልጠበቀችው  መንገድ  ለዛውም  በቀላሉ

አግኝታለች፡፡ፀሀፊነት፡፡ስራውን ያገኘችላት..በፊት ትሰራበት የነበረ ፀጉር ቤት በደንብኝነት ታውቃት በነበረች አስቴር በምትባል ሴትዬ አማካይነት ነው፡፡
‹‹እማዬ በቃ እሷንም ሆስፒታል ወስደን ማሳከም እንችላለን ..ብዙ ብር ነው፡፡››
‹አዎ እንደዛ ብያት ነበር..ግን ቦርሳዋ ውስጥ ብዙ ብር አለ ….ይሄንን ለቤት የጎደለ ነገር ግዙበት መታከም ከፈለኩ በዚህ እታከማለው አለችኝ…››አብራሩላት
‹‹ውይ እማዬ እንደዛ ከሆነ ደስ ይላል..አሁን ምን እናድርገው››
‹‹እኔ እንጃ የጠራሁሽ ለዛ ነው…አንቺ ያስፈልጋል የምትይውን ነገር ለቤቱም ለእሷም ገዝተሸ ነይ፡፡››
‹‹አዎ ትክክል ነሽ እማዬ ››አለችና ብሩን ከእጃቸው ላይ ተቀብላ ግማሹን ገመሰችና‹‹..ይሄንን አስቀምጪው..በዚህ የሚያስፈልገንን ነገር ገዝቼ መጣለሁ...ዝም ብለን ብሩን ታቅፈን ከጠበቅነው አባዬ ሁንም ተቀብሎን ነው የሚመልስላት››ስትል ስጋቷን ነገረቻቸው፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

30 Dec, 18:49


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ስምንት

ሰለሞን ለዚህ ነው ከውጭ ከተመለሰ በኃላ ለመደላደል ስራ መጀመር እንዳለበት የወሰነው
‹‹ምንድነው መስራት ያለብኝ?ምን አይነት ዕውቀት ነው ያለኝ?ምን አይነት ጥሪትስ አለኝ?ህብረተሠብስ ምን አይነት ሸቀጥ ወይም አገልግሎት ነው መግዛት የሚፈልገው?። መልሶቹ ቀላል አልነበሩም...ወደ አእምሮው የሚመጣው መልስ ወደግል ስራ የሚያስገባው ሳይሆን እንደውም በተቃራኒው የሚያርቀ ነው የሆነበት።
1/ይሄ የምኖርበት ህብረተሠብ በዚህ ሰአት ግዙፍ ችግሩ ምንድነው...?ወረቀትና እስኪሪብቶ ያዘና ዘርዝሮ መፅፍ ጀመረ
1/ኑሮ ውድነት
2/የሠላም እጦት
3/የፍቅር እጦት
4/ቴክኖሎጂ ቅኝ ግዛት
5/...!!የአየር ፀባይ መዛባት
የፃፈውን መለስ ብሎ አየው ...ለደቂቃዎች ብቻውን ተንከትክቶ ሳቅ ። ዝርዝሩን አንድ አነስተኛ የግል ቢዝነስ ለመክፈት ሳይሆን አዲስ ጠቅላይ ሚንስቴር ሆኖ ተሹሞ በሀገሪቱ ስር ነቀል ለውጥ የሚያመጡ የፓሊሲ አማራጮችን ለማርቀቅ መነሻ ሀሳቧችን እያሰላ ያለ ፓለቲከኛ ነው  የሚመስለው።
‹‹እስቲ የህብረተሠብም የኑሮ ውድነትን የሚቀርፍ ምን አይነት ቢዝነስ ነው የሚኖረው...?ኑሮ ውድነቱ እንኳን ግለሠብ መንግስትስ ለማስተካከል አቅም አለው...?የመለኮት ጣልቃ ገብነት ከሌለስ  መፍትሄ ይኖረዋል?።››ሲል አሰበና በራሱ ድርጊት ዳግመኛ ሳቀ፡፡ ከዘረዘራቸው ሀሳቦች የ3 ተኛው ሀሳቡን ገዛው።‹‹ፍቅር እጦት የእኔም የማህበረሰብም የጋራ ችግር ነው።የፍቅር እጦት ደግሞ የሌሎች ችግሮች ሁሉ መነሻ ምክንያት ነው።ደግሞ በሙሉ አቅሜ መስራት የምችለው ስራ እሱን ነው …ሞያዬም ችሎታዬም እሱ ላይ ነው››ሲል አሰበና ወሰነ፡፡

አሜሪካ እያለ ተቀጥሮ የሚሰረባትን የፍቅርና የጋብቻ አማካሪ ድርጅት እዚህ ሀገሩ መሀል አዲስ አበባ ላይ በራሱ ለመክፍት ወሰነ…‹‹የራስህን ቢዝነስ ጀምር›› ብላ ስትጨቀጭቀው ለነበረችው አስቴር ነገራት፡፡፡አንገቱ ላይ ተጠምጥማ ጉንጩን እየሳመች በሀሳብ በጣም መደሰቷንና በማንኛውም ነገር ከጓኑ እንደሆነች አበሰረችው…እሷ የተደሰተችበት ነገር ደግሞ በእሱ ህይወት ትልቅ ቦታ ስላለው ወዲያውኑ በደስታ ወደእንቅስቃሴ ገባ……ፍቃድ ለማውጣት ቢሮ ለመከራየትና አስፈላጊ የቢሮ እቃዎችን አሞልቶ ለመክፈት 40- ቀን ብቻ ነበር የፈጀበት፡፡

ይሁን እንጂ ለአንድ ወር ያህል በሰአት ቢሮ እየገባ በሰዓት ቢወጣም አንድም ደንበኛ ማግኘት አልቻለም…ሁሉ ነገር ተስፋ አስቆራጭ የሆነበት፡፡ግራ ጋባው ፣በመጀመሪያውም ዝግና ድብቅ ባህል ባለበት ሀገር የጋብቻና የፍቅር አማካሪ ድርጅት ከፍቶ ውጤታማ ሆናለው ብሎ በማሰብ በራሱ ጅልነት ተበሳጨ…የስድስት ወር የቢሮ ኪራይ ባይከፍልና ለፈርኒቸር እና የቢሮ እቃዎችን ለማሟላት ከመቶ ሺ ብሮች በላይ ባያወጣ ኖሮ ሁሉን ነገር እርግፍ አድርጎ ዘጋግቶ ሌላ የቅጥር ስራ ይፈልግ ነበር..ግን ለጊዜው እንደዛ ማድረግ አይችልም…‹‹አዎ ለአስቴር ምን እላታለሁ….?እንድታፍርብኝማ አላደርግም…እሷ ከምታፍርብኝ አለም ጠቅላላ ብትገለባበጥ እመርጣለሁ….ስለዚህ የሆነ ነገር ማድረግ አለብኝ››በማለት ወሰነና ቀኑን ሙሉ ሲያሰላስል ዋለ… የሆነ ነገር ብልጭ አለለት፡ስልኩን አነሳና ደወለ፡፡
ከአራት ጥሪ በኃላ ተነሳ፡፡
‹‹ሄሎ ወንድሜ….›››የሚል ድምፅ በስልኩ እስፒከር አቆርጦ ጆሮው ውስጥ ተሰነቀረ…
‹‹አለሁልሽ››
‹‹ምነው ድምፅህ?››
‹‹ደህና ነኝ….የሆነ ነገር ላማክርሽ ነበር?››
‹‹ይቻላል..ግን ስራ አሪፍ ነው እንዴ?….››
‹‹አሪፍ ነው …አሁን አንድ ደምበኛዬን ወደትዳር ከመግባቷ በፊት ማድረግ ስለሚገባት ቅድመ ዝግጅት ማወቅ ፈልጋ ነበር.. እሷን እንደሸኘሁ ነው የደወልኩልሽ››ዋሻት፡፡
‹‹ደስ ይላል ወንድሜ …ህልምህን መኖር ጀምረሀል ማለት ነው….››
‹‹አንቺ ከጎኔ ሆነሽ እስከደገፍሺኝ ድረስ ምንም ማላሳከው ነገር የለም…..አሁን ለምን መሰለሽ የደወልኩልሽ…ፀሀፊ ብቀጥር ብዬ አሰብኩ…››ያሰበውን ነገራት፡፡
‹‹አዎ አንተ ….እስከዛሬ እንዴት አላሰብንበትም…?ለፕሮቶኮሉ እራሱ አስፈጊ ነው…ባለጉዳዬች እንደመጡ አንተን ማግኘት የለባቸውም በፀሀፊህ በኩል ቀጠሮ ይዘውና ተገቢውን ቅድመ ማሟላት ያለባቸውን ነገር አሟልተው መሆን አለነበት…አሪፍ ነው…››
‹‹እና እንዴት ላደርርግ ?ማስታወቂያ ላውጣ….?››
‹‹አይ እኔ በሶስት ቀን ውስጥ ምርጥ ፀሀፊህ ቀጥርልሀለው….አንተ በዚህ ጉዳይ ምንም አትጨነቅ…..ሶስት ቀን ብቻ ስጠኝ››
‹‹እሺ ማታ እቤት እንገናኝ››
‹‹እሺ ቸው ..ወንድሜ››
‹‹ቸው..››
ወንድሜ የሚለው ቀል ከአንደበቷ በወጣ ቁጥር በአንገቱ የተንጠለጠለ የብረት ሰንሰለት ነው የሚታየው….ሆነ ብላ እሱን ለማጥቃት አስባ ከአንደበቷ የምታወጣው ነው የሚመስለው….‹‹አደራ እኔ እህትህ ባልሆንም ልክ እንደእህትህ ነኝና ሌላ ነገር በአእምሮህ እንዳይበቅል››የሚል ማስጠንቀቂያ ነው የሚመስለው፡፡
የእናትና አባቱ ልጆች የሆኑት እህቱ ወንድሜ የሚለውን ስም በአመት አንዴ እንኳን ሲጠቀሙ አልሰማም….ትዝም የሚላቸው አይመስለውም…እሷ ግን ልክ እንደዘወትር ፀሎት እንደውዳሴ ማርዬም ነው በየእለቱ የምትደግመው፡፡
///
በፀሎት ጥዋት ከእንቅልፏ ስትባንን እቤት ውስጥ ከወ.ሮ እልፍነሽ በስተቀር ሌላ ማንም ሰው አልነበረም፡፡
‹‹እማዬ ሰው ሁሉ የት ሄደ?››እማዬ ብላ መጣራቷን ለራሷም እየገረማት ነው…ደግሞ አፏ ላይ አልከበዳትም…ወላጅ እናቷ…ሌላ ሴት እናቴ እያለች መጥራት መጀመሯን ብትሰማ ልብ ድካም ይዟት ፀጥ እንደምትል እርግጠኛ ነች፡፡
‹‹ወይ ልጄ… ነቃሽ…ልቀስቅሳት ወይስ ትንሽ ትተኛ እያልኩ ከራሴ ጋር ስሟገት ነበር፡፡ በረሀብ ሞትሽ እኮ››ብለው  ወደ ጓዲያ ገብና የእጅ  ማስታጠቢያ  ይዘው መጥተው

ሊያስታጥቦት ጎንበስ አሉ…እንደምንም ከአንገቷ ቀና ብላ ተነሳችና ‹‹ያስቀምጡት እኔ እታጠባለው››
‹‹አረ ችግር የለውም ልጄ ..ችግር የለውም››
‹‹ግድ የሎትም….››.
‹‹እንግዲያው ታጠቢ …ቁርስሽን ላቅርብ ›› ብለው ማስታጠቢያው ስሯ አስጠግተው አስቀመጡላትና ተመልሰው ወደ ጓዲያ ሔድ …….እግሯ በተንቀሳቀሰች ቁጥር ጥዝጣዜው ነፍሶ ድረስ ይሰማታል…..ፊቷ ላይ አሁንም ተራራ የሚያህል ቁስል የተሸከመች እየመሰላት ነው…እንደምንም ተንፏቀቀችና እጇን ታጥባ የሚመጣላትን ቁርስ መጠበቅ ጀመረች…ጩኮ ከእርጎ ጋር ነበር የመጣላት…ጩኮ መች በልታ እንደምታውቅ አታስታውስም….ቤቷ ቁርስ ሲቀርብ አስር …አስራአምስት አይነት ምግብ ጠረጴዛ ሞልቶ ነው….ከዛ ውስጥ ሶስት ወይም አራት አይነቱን አፕታይቷ የፈቀደላትን መርጣ በልታ ሌላውን ትተዋለች..አሁን የቀረበላት ምግብን ያህል ግን አስደሳች አልነበረም…….እርቧት ስለነበረ እየተስገበገበች በላች…
ያጋባችውን ሰሀንና ብርጭቆ መልሳ…እጇን ታጠበችና…..‹‹እማዬ ማንም የለም እንዴ?››ስትል ደግማ ጠየቀች፡፡
‹‹ልጄ ለሊሴ ስራ ፍለጋ ብላ ወጥታለች…ፊራኦል ስራ ነው ..አባትሽም እንደዛው››መለሱላት፡፡
‹‹ለሊሴ ምን አይነት ስራ ነው የምትፈልገው?››

ከመጽሐፍት መንደር💠

30 Dec, 15:34


📚ርዕስ : " አልፀፀትም
📝ፀሀፊ: " ጃዋር መሀመድ

📖የገፅ ብዛት:- 433
📆ዓ. ም:-.. 2017

▬▬▬▬▬▬▬


        https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal

ከመጽሐፍት መንደር💠

25 Dec, 17:55


ግን ደግሞ የአስቴር ወቅታዊ ኩርፊያ አልገባውም ነበር።‹‹መስፍን ደብዳቤ ለፃፈላት እኔን ለምን ልታኮርፈኝ ቻለች?››እራሱን ጠየቀ
"እና እኔ ምን አጠፋው..የምታኮርፊኝ?"ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡ "አይ አንተማ ምንም አላጠፋህ …እኔ ነኝ እንጂ ዘላለም በብላሽ ከአንተጋር የምንዘላዘለው..ነው ወይስ እናቴ የቤታችሁ አገልጋይ ስለሆነች አትመጥነኝም ብለህ አስበህ ነው?"አለቸው።እና እየተመናጨቀች ተለይታው ወደቤቷ አመራች።
ሰለሞንም ደንዝዞ ወደቤቱ ገባና በመጨረሻ ስትለየው የተናገረችውን ዓ.ነገር ሲያሰላስል አደረ።"....እኔ ነኝ እንጂ ዘላለም በብላሽ ከአንተጋር የምንዘላዘለው... ‹‹ምን ለማለት ፈልጋ ነው?ታፈቅረኛለች ማለት ነው?እኔስ አፈቅራታለሁ እንዴ? መስፋን የፃፈላትን ደብዳቤ ሳነብ ለምን ቅር አለኝ,,,?ቀንቼ ነው እንዴ?ፍቅር ሲይዝ እንዴት ነው የሚያደርገው?ስምንተኛ ክፍል ሆኖ ፍቅረኛ መያዝ ይቻላል እንዴ?››እነዚህንና መሰል ጥያቄዎች ባልጠና እና ለጋ ጭንቅላቱ ሲያወርድና ሲያወጣ እንዲሁ እንቅልፍ በአይኑ ሳይዞር ነጋ...፡፡ከዛን በኃላ በማግስቱ አናገራት ….እንደሚያፈቅራትና እሷ ፍቃደኛ ከሆነች ፍቅረኛው እንድትሆን እንደሚፈልግ ነገራት..እሷም በደስታ ፈንጥዛ እላዩ ላይ ተጠመጠመችበት….ከዛ የታዳጊነት ፍቅራቸው እስከ አስረኛ ክፍል ቀጠሉ…የበለጠ ጊዜ በሄደ መጠን በእነሱም መካከል ያለ ፍቅር እየደረጀና ስር እየሰደደ መጣ፡፡አስረኛ ክፍል በጀመሩ በሶስተኛው ወር አንድ ቀን ጥዋት የትምህርት ቤት ሰዓት ደርሶ ቀድሞ ወጥቶ ቢጠብቃት ልትመጣ አልቻለችም...ተማሪ ሁሉ ሄዶ ማለቁንና ሰዓቱ መርፈድንም ከግንዛቤ በማስገባት በለሊት ቀድማ መሄዶን ጠረጠረና በሩጫ ወደትምህርት ቤት...በረፍት ሰዓት ክፍሏ ሄዶ ቢያያት እንዳልመጣች ጓደኞቾ ነገሩት።ግራ ተገባ።
አስቴር ከትምህርት ቤት በቀላሉ የምትቀር አይነት ልጅ አይደለችም። ለትምህርቷ የምትሰጠው ትኩረት ቀላል የሚባል አንዳልሆነ ያውቃል…ታዲያ እንዴት?።እናም ያለ መምጣቷ ዜና አልተዋጠለትምና እሱም እንዳመመው በመናገር አስፈቅዶ ወደቤት ሄደ…ወደቤት የሄደበት ዋና ምክንያት የአስቴር እናት እንጀራ ልትጋግር ወይም ሌላ ስራ
ለመስራት ወደእነሱ ቤት የምትመጣበት ቀን ስለሆነ አስቴር ለምን እንደቀረች ሊጠይቃት ነበር እቅዱ፡፡እቤት ሲደርስ ግን ማንም አልነበረም..የአስቴር እናትም እንዳልመጣች በኩሽናው መቆለፍ አረጋገጠና ደብተሩን አስቀምጦ ወጣና ወደ እነአስቴር ቤት አመራ… ሰፈራቸው ሲደርስ እቤታቸው ፊት ለፊት ድንኳን ተተክሎ ነጠላ ያዘቀዘቁ ሴቶችና ጋቢ የደረብ ወንዶች ሲተረማመሱ ከሩቅ አየ...ሰውነቱ እስኪንቀጠቀጥ ድረስ ነው የደነገጠው፡፡
‹‹አስቱካ ምን ሆነች?››በሩጫ ነበር ተንደርድሮ ድንኳኑ መሀከል የተገኘው...አስቴር በአራት በሚበልጡ ሴቶች ግራና ቀኝ ተደግፋ ‹‹ወይኔ እናቴ እያለች›› ስትንፈራፈር ተመለከታት"ተመስገን"አለና ትንፋሹን ወደውስጥ እየሳበ ለመረጋጋት ሞከረ።‹‹ተመስገን
››ያለው እናቷ ስለሞቱ አይደለም...በፍፁም ።ይልቅ እሷ በህይወት ስላለችልለት ተደስቶ ነው።እንጂማ እናቷ ከህፃንነቱ ጀመሮ ከገዛ እናቱ በመቀጠል ያሳደጉት ያዘሉትና የመገብት ሴት ናቸው…….የእሳቸውም ሞት በጣም አስደንግጦታልም አሳዝኖታልም…
ከዛ ከሀዘን ቤት እስክትወጣም ሆነ ከዛ በኃላ ከስሯ አልተለየም።ግን እሷን ማፅናናት እና ወደ ህይወቷ እንድትመለስ ለማድረግ ቀላል አልሆነለትም።ምክንያቱም ለአስቴር እናቷን ማጣት እናትን ብቻ ሳይሆን መላ ዘር ማንዘሯን ማጣት ማለት ነበር።ምክንያቱም አባቷን ጭራሹኑ እሷ እንደተፀነሰች የሞተ እና ዘመዶቹንም የማታውቅ ሲሆን በተመሳሳይ እናቷም የረባ የቅርብ ዘመድ ያልነበራት ብቻዋን ወልዳ ብቻዋን ያሳደገቻት ነበረች እና እሷም ስትሞትባት ሌላ አይዞሽ የሚላትና የሚያፅናናት አንድም የቅርብ ዘመድ አልነበራትም።በኃላ የእናትና አባቱ ተማከሩና አስቴርን እንደልጃቸው አድረገው ወደቤታቸው አመጧት፡፡
ትዝ ይለዋል የአስራ አምስት አመት ልጅ እና የአስረኛ ክፍል ተማሪ እያለ ነበር…አስቴር የቤተሰቡ አባል ሆና የተቀላቀለች፡፡አዎ እሷ ስትመጣ እሱ ከእህቱ ጋር ከሚጋራው ክፍል ተፈናቀለና ሌላ ትልቁ ወንድሙ ለቆ ዩኒቨርሲቲ በገባበት ክፍል ከአመፀኛው ወንድሙ ጋር ደባል ሆኖ ገባ…
እድሜውን ሙሉ የኖረበትን ክፍልና የተኛበትን አልጋ እንዳለ ለአስቴር አስረከበ….እንደዛ በመሆኑ አልከፋውም….፡፡ለሌላ ሰው ልቀቅ የተባለ ቢሆን ኖሮ ከፍተኛ አብዬት ያስነሳ እንደነበር እርግጠኛ ነው….ለአስቴር ስለሆነ ግን እንደውም ደስ ያለው ይመስላል…እርግጥ እሱ ከመኝታው ሳይፈናቀል በእሱ ምትክ እህቱ እንድትለቅላት ቢደረግ ወይንም ሌላ ሶስተኛ አልጋ ወደክፍሉ እንዲገባ ተደርጎ እሷ እንድትተኛ ቢደረግ በጣም ደስተኛ ይሆን እንደነበር እርግጠኛ ነው..ግን ለምን ተብሎ ሊጠየቅ የማይችለው አባቱ ኮስተር ብሎ የወሰነው ውሳኔ ስለሆነ ያለምንም ማቅማማት ነው ተግባራዊ የሆነው፡፡
አስቴር ከእሱ በአንድ አመት ስትበልጥ ከእህቱ ስህን ደግሞ በሁለት አመት ታንሳለች…..ስለዚህ የሁለቱንም ጓደኛ ነች፡፡
ይሄ ውሳኔ በደስታ እንዲፈነጥዝ እና በወላጆቹም እንዲኮራ አደረገው።እና እህቱም ጓደኛውም ሆነች...።የነካኩት የፍቅር ጉዳይ ግን እንደተዳፈነ ቀረ...።
አስቴር ‹‹ እቤታቸውንም ልባቸውንም ከፍተው እንደገዛ ልጃቸው የተቀበሉኝን ሰዎች ልጃቸው ጋር ባልጌ አላሳዝናቸውም…እኔ እና አንተ ከአሁን በኃላ እህትና ወንድም እንጂ ፍቅረኛሞች መሆን አንችልም›› ብላ ቁርጥ ያለ ውሳኔዋን ነገረችው፡፡እሱ በቀላሉ ውሳኔውን ሊቀበል አልቻለም፡፡ይበልጥ ሊያጣት እንደሆነ ባወቀ ቁጥር ውስጡ የንዴት እሳት እየነደደ ይለበልበው ጀመር፡፡
እና ውሳኔዋን እንድትቀይርና እንድታስተካክል በወጣች በገባች ቁጥር ሲያስቸግራት እሷም እሱን ተስፋ ለማስቆረጥ እርምጃ ወሰደች…ስምንተኛ ክፍል ሆነው ደብዳቤ የፀፈላትን መስፍንን 11 ክፍል ፍቅረኛ አድርጋ ተቀበለችው፡፡
ከዛሬ ነገ እሱን ትታ ወደእኔ ትመለሳለች ብሎ በትእግስ ሲጠብቅ ሁለቱም 12ተኛ ክፍል ማትሪክ ተቀበሉና ዩኒቨርሲቲ ገቡ…ልክ በተመረቁ በ3ተኛ ወሯ መስፍን እነ ሰለሞን ቤተሰቦች ጋር አስቴርን ለማግባት ሽማጊሌ ላከ…ወዲያው ቀለበት አሰሩና ከሶስት ወር በኃላ ተጋቡ፡፡
በዚህን ጊዜ ሰለሞን ሁሉ ነገር አስጠላው…ሁሉን ነገር ጣጥሎ በትምህርት አሳቦ ወደውጭ የተሰደደበት ዋና ምክንያት የእሷ ማግባት ነበር…ለአመስት አመት እዛው ኖረና ድንገት ለመመለስ ወሰነ…ይሄንን ወደሀገር የመመለሱን ውሳኔ የወሰነበት ዋናው ምክንያትም  አስቴር ከ5 አመት የጋብቻ ቆይታ እና አንድ ልጅ ከወለዱ በኃላ ተፋተው እሱም ልክ እንደእሱ አገር ጥሎ እንደተሰደዱ ስለሰማ ምን አልባት ከአመት በፊት የተነጠቅኩትን ፍቅሬን መልሼ የማግኘት እድል ይኖራኛል በሚል ተስፋ ነበር የተመለሰው፡፡ከልጅነት እስከጎልማሳነት የዘለቀ እንቅፋት የበዛበት ውስብስብ ፍቅር…እና ሁሉ ጊዜ ስለራሱና ስለፍቅሩ ሲያስብ ‹‹ጠንቆይ ለራሱ አያውቅም እያለ ››ይተርታል..፡፡
እሱ ለላፉት ሶስትና አራት አመታት ለብዙ ሺ ጥንዶች እንዴት ያፈቀሩትን ሰው ማሳመንና የራሳቸው ማድረግ እንዳለባቸው..ፍቅራቸውን እንዴት መንከባከብ እንደሚገባቸው ውጤታማ ምክር እየሰጠ ተግባራዊ እንዲያደርጉት ሲጫናቸውና ደከም ያሉትንም ሲበሳጭባቸው ከርሞል..ግን የራሱን ከልጅነቱ ጀምሮ ሲያበቅለውና እየተንከባከበ ሲያሳድገው የነበረውን ፍቅር የሆነ ዘዴ ፈጥሮ ፍሬውን ለመብላት ፈፅሞ አልቻለም፣አሁን ግን ቆርጦ ነው የመጣው አዎ

ከመጽሐፍት መንደር💠

25 Dec, 17:55


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሰባት

/
ስራው "የፍቅርና የጋብቻ አማካሪነት ነው።የተማረው ፍልስፍና ነው።ሁለተኛ ዲግሪውን ግን አሜሪካ ሄዶ በስነልቦና መስራት ችሏል፡፡በፍቅርና ጋብቻ አማካሪነት የሰራውም አዛው አሜሪካ ነው….ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኃላ ሶስት አመት ተቀጥሮ ሰርቶል፡፡አሜሪካዊያኑ በፍቅርና በጋብቻ ጉዳይ ችግር ሲያጋጥማቸው ባለሞያ ጋር መሄድና ድጋፍ ማግኘት ባህላቸው ነው፡፡በመጀመሪያ ወደትዳር ከመግባታቸው በፊት ማድረግ ስለሚገባቸው ስነልቦናዊ ቅድመ ዝግጅት ለማወቅ ባለሞያው ጋር ይሄዳሉ..ትዳር ውስጥ ገብተው ችግር ሲያጋጥማቸው…እርስ በርስ ያለው ተግባቦታቸው አመርቂ ካልሆነ…የቤተሰብ ጣልቃ ገብነት የሚያጨቃጭቃቸው ከሆነ…የወሲብ አለመጣጣም በመሀከላቸው ካለ ብቻ ማንኛውንም ችግር በመሀከላቸው ከተፈጠረ ወደጋብቻ አማካሪ ሄዶ ሞያዊ ምክር መጠየቅና ከዛም የሚሰጣቸውን ምክርና ትዕዛዝ ለየብቻም ሆነ አንድላይ በመተግበር ችግሩን ለመቅረፍ የሚያደርጉት ጥረት ያስቀናል፤ሌላው ይቅር ጋብቻቸው እንደማይሰራ እርግጠኛ ከሆኑ እንኳን ጤናማና ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዴት መለያየትና ጓደኛሞች ሆኖ መቀጠል እንደሚችሉ ምክር ለማግኘት ተያይዘው ወደ ጋብቻ አማካሪ ቢሮ ይሄዳሉ..ይህ ጉዳይ በጣም ነበር የሚያስገርመው፡፡በተለይ በመሀከላቸው ልጆች ካሉ ለየብቻ ሆነው እራሱ
የልጆቻቸውን ስነልቦና ጠብቀው እንዴት ተግባባተው ማሳደግ እንዳለባቸው ዝርዝር መመሪያ ከአማካሪዎች በመስማት ያንን ሳያዛንፉ በመተግበር የልጆቻቸውን ደስታ ሆነ የእነሱን ሰላም ይጠብቃሉ፡፡ያም ሆኖ ግን ምንም እንኳን በስራው በጣም ደስተኛና ጥሩ ገቢ የሚያገኝበት ቢሆንም ከአምስት አመት በኃላ ጠቅልሎ ወደሀገሩ ተመለሰ….ሲሄድ መቼም ላይመለስ ነበር…..ሀገር ቤት ባሉ ነገሮች ጠቅላላ ተስፋ ቆርጦ ነበር…ግን እንዲመለስ የሚያስገድደው ቁራጭ ምክንያት አገኘ……እና ተመለሰ፡፡
ሰለሞን ወደሀገር ቤት እንደተመለሰ መጀመሪያ ተቀጥሮ ለመስራት  ስራ ለማፈላለግ ሞክሮ ነበር….።አስቴር ግን የራሱን ስራ መጀመር እንዳለበት በተደጋጋሚ ጊዜ ግፊት ስታደርግበት እራሱን ከተበታተንበት ሰበሰበና እና መኝታ ቤቱ ውስጥ ገብቶ በላዩ ላይ ዘጋና ስብሰባ ተቀመጠ።አስቴር የልጅነት ጓደኛው እናም ደግሞ ፍቅሩ ነች…ወጣት ሲሆኑ ደግሞ እህቱ ሆነች…እስከአሁንም እህቱ ሆና ቀረች..እሱ በልቡ ተመልሳ ፍቅሩ እንድትሆን ነው የሚመኘው….አላማውም እቅዱም ያ ነው..እሷ ግን ያንንን መስመር ጠርቅማ ዘግታበት አባቱን አባቷ እናቱን እናቷ አድርጋ ለእሱ ደግሞ እህቱ ሆናለች፡፡
ከልጅነቱ ጀምሮ ነው የሚያውቃት፡፡ ገና ሰባት ወይ ስምንት አመቱ ላይ…የእናቷን ጠርዙ የነተበ የቀሚስ ጫፍ በትናንሽና ለስላሳ እጆቾ ጨምድዳ ይዛ ስርስሯ ኩስ ኩስ እያለች ስትመጣ ነበር የሚያውቃት…የዛን ጊዜውን የልጅነት መልኳን አሁንም በአእምሮው ሰሌዳ ላይ በጉልህ ተስሎ ይገኛል..በአጭሩ ተቆርጦ እርስ በርሱ ተጠቅልሎ የተንጨፈረረ ወርቃማ ፀጉር…ጎላ ጎላ ብላው በፍርሀት የሚንካባለሉ አይኖች…በእንባና በአቧራ ብራብሬ የሆነ አሳዛኝ ፊት….ልክ የግቢው አጥር ተከፍቶላቸው የፊትለፊቱን ትልቁን የሳሎን በራፍ አልፈው ወደጓሮ ሲዞሩ ከኃላ ተከትሎቸው ይሄዳል…እናትዬውን ተከትላ ማድቤት ስትገባ ተከትሏቸው ይገባል…
‹‹የእኔ ልጅ፣ እስኪ እኔ ስራዬን ልስራበት አንቺ ከሰሎሞን ጋር አብራችሁ ተጫወቱ››እያለች እናትዬው ታባብላታለች…እሷም የእናትዬውን ልመና ተቀብላ ከእሱ ጋር ለመጫወት ፍቃደኛ እንድትሆን በአይኖቹ ጭምር ይለማመጣታል….የተቋጠረ ግንባሯን ሳትፈታ በቀሰስተኛ እርምጃ ወደእሱ ትጠጋለች…በደስታ አጇን አፈፍ አድርጎ ይይዛትና እየጎተተ ወደትልቁ ቤት ይዞት ይሄዳል…ከታላቅ እህቱ ጋር በጋራ ወደሚኖርበት መኝታ ክፍላችው ይዞት ይገባል፣..ያሉትን መጫወቻዎች ሁሉ ከየመደርደሪያዎቹን ከየአልጋ ስሩ እየጎተተ ያወጣና  ፊት ለፊቷ  ወለሉ  ላይ  ይቆልላል፣ለእሱ  የሰለቹትን  መጫወቻዎች  ለእሷ  ብርቆ
ነበሩ….እናትዬው እነሱ ቤት በተመላላሽነት በሳምንት ሶስት ቀን ትሰራለች፡፡እና እነዛን ሶስት ቀናት በናፍቆትና በፍቅር ነበር የሚወዳቸው… ሳምንቱን ሙሉ ለምን እንዳማይመጡ ይገርመው ነበር..ከዛ አባቱ እሱን አንደኛ ክፍል አስመዝግቦ ትምህርት ሲያስጀምረው ለእሷም እንደዛው ደብተርና ዩኒፎርም ገዝቶ እሱ የሚማርበት ትምህርት ቤት እናቷ እንድታስመዘግባት አደረገ…አንድ ትምህርት ቤት አንድ ክፍል መማር ጀመሩ…ይሄ ደግሞ የሚገናኙበትን የቀን ብዛትና አጋጣሚ አሰፋው…..ጓደኝነታቸው አብሮ ዕቃ ዕቃ ከመጫወት የተጀመረ ….ከዛ ኤለመንተሪ ጀምረው እስከ ሀይ እስኩል በተመሳሳይ ጊዜ በተመሳሳይ ክፍል ውስጥ ነው የተማሩት።የተወሰኑ ክፍሎችን አንድ ክፍል ጥቂት ክፍሎችን ደግሞ አንድ መቀመጫ ላይም አብረው ተቀምጠው የመማር አጋጣሚዋች ነበሯቸው።ስለዚህ እሷ ልክ አብረውት እንደተወለድ ወንድሞቹ እና እህቱ እድሜ ልኩን ነው የሚያውቃት፡፡
ፍቅር የጀመሩት 8ተኛ ክፍል ሲማሩ ነው።በወቅቱ እሱ 8ተኛ ቢ ሲማር እሷ ደግሞ 8ተኛ ኤፍ ክፍል ነበረች።ግን ቢሆንም ብዙውን ጊዜ ወደት/ቤት ሲሄድና ወደሰፈር ሲመለሱ ተጠራርተውና ተጠባብቀው ነበር።እና አንድ ቀን ከትምህርት ቤት ሲወጡ እየጠበቀችው ነበር።አብረው ወደቤት መመለስ ቢጀምሩም ግን አንደበቷ እንደተቆለፈና እንደተበሳጨች ነበር...ምን እንደሆነች ቢጠይቃትም በቀላሉ ልትነግረው አልቻለችም..በኃላ በስንት ጭቅጭቅ ከባርሳዋ አንድ ወረቀት አውጥታ ሰጠችው።ምንድነው? ብሎ በጉጉት ተቀብሎ አነበበው።
አስቴርዬ የእኔ ቆንጆ..የፍቅርሽ ፍላፃ ልቤ ላይ ነው የተሰካው….እስካሁን ሰንኮፉን
አልነቀልኩትም…ያልነቀልኩት ሲሰካብኝ ከነበረው ጊዜ በላይ ስነቅለው ያመኝ ይሁን በሚል ስጋት ነው…….ምን አልባት አንቺው በትንፋሽሽ አዘናግተሸ በልስልስ እጆችሽ ቀስ ብለሽ ብትነቅይልኝ መልካም ይሆን ይመስለኛል፡፡፡አንቺ እኮ ከአለም ሴቶች ጭምር ተወዳዳሪ
የሌለሽ ውብ ነሽ።እኔ አፍቃሪሽ በአንቺ ፍቅር መንገላታት ከጀመርኩ አመታት አልፈዋል።ግን እስከዛሬ ስቃዬን በውስጤ አፍኜ ህመሜን የቻልኩት ከጓደኛዬ ከሰለሞን ጋር ግንኙነት ያላችሁ ስለሚመስለኝ ነበር።ግን በቀደም ወኔዬን አሰባስቤ ስጠይቀው ጓደኛሞች ብቻ እንደሆናችሁ ነገረኝና ነፍሴን በሀሴት አስጨፈራት።እና ውዴ አንቺስ ምን ትያለሽ...
?መልስሽን በጉጉት እጠብቃለሁ... የአንቺው አፍቃሪ መስፍን ጋዲሳ›› ይል ነበር።
አነበበውና ግራ የመጋባትና የመደነጋገር ስሜት ተሠማው..በደብዳቤው ላይ እንደተጠቀሰው በቀደም በብዙ ጓደኞቻቸው መካከል ስለፍቅር አንስተው ሲያወሩ መስፍን እንደቀልድ ‹‹አስቴርና ሰለሞን ፍቅረኛሞች ናቸው›› አለ ወዲያው ሰለሞን ከአፉ ተቀበለና
‹‹እውነት አይደለም እኔና አስቴር ፍቅረኛሞች ሳንሆን ጓደኛሞች ነን ››ብሎ መልስ ሰጠ
።ነገሩ በዚህ ተደመደመ።ደብዳቤውን ባነበበበት ወቅት ግን መሠፍን ሆነ ብሎ ለገዛ የግል ጥቅሙ ጥያቄውን ጠይቆት እንደነበረና እሱንም ማኖ እንዳስነካው ገባውና በጅልነቱ ተበሳጨ።

ከመጽሐፍት መንደር💠

24 Dec, 04:40


አቦ.. እግዜር ተወኝ
'
'
ለምንድነው የማትጠራኝ
ለምንድነው የጠፋሁት
ቅዳሴው ሲሰማኝ
ቢራ ቤት ነው የነበርኩት

ለምን ከፋኝ በጭስ መሃል
ሳየው ያንተን የአምላክ ምስል ፣
መከራም እንዲህ ነው
ባለበት እዳ ነው አምላኩን የሚስል ፣

በቢራው አራፋት
በጃምቦው ብርጭቆ
ሀዘንህ ሲታየኝ ፣
ጨልጬ ብጠጣው
የማላይህ መስሎኝ ፣

ባዶ እስኪቀር የስካሬ ሞራል ፣
በማላውቀው ታምር
በማውቀው ቤተስኪያን
ድምፅህ ልጄን ይላል ፣

ለምን

ለምን እኔን ጠራህ
አሉህ አይድል በአጥርህ ፈርጡ
እነሱን ያዛቸው እኔን እንደሆነ
የለሁ ካጥረ ገጡ ፣

ተወኝ ልጠጣበት
ተወኝ አታሰማኝ የእርጋታህን ቃል ፣
ሙዚቃ ስጨምር ጭፈራ ሳበዛ
ለሽንት እንደወጣሁ
ያንተ ድምፅ ይሰማል ፣

ለምን...?እኔ መረጥክ
ተወኝ እግዜር ባክህ
ተወኝ ተወኝ አቦ ፣
አንድ በግ ስትፈልግ
ጠፍተው እንዳይቀሩ
ያሉልህ በደቦ ፣

እንዲህ ስናገር በሲጃራው መሃል
በጭሴ ውስጥ ቅርፁ
ያንተን መልክ ያሳያል

በስካሬ መሃል ይታየኛል እኔ
የሰከረ አምላክ የሰከረ ምስል ፣
አምላክም እንዲህ ነው
ባለበት እዳ ነው ጠፊ ልጁን ሚስል ፣

'
ግዕዝ ሙላት 🦘

ከመጽሐፍት መንደር💠

23 Dec, 20:10


‹‹እንዴ ብቻዬን ልቆይ እኮ አይደለም ያልኩህ ..አንተ ምትገባ ከሆነማ እኔ ብቻዬን ፈራለሁ›
‹‹በለሊት ሞተር ስትጋልቢ እንዴት ሳትፈሪ…?ለማንኛውም ወንበር ላመጣልሽ ነው››አለና ወደቤት ገባና አንድ ባለመደገፊያ ወንበር በማምጣት አደላድሎ ወስዶ አስቀመጣትና ከጎኗ ጠፍጣፋ ድንጋይ አስቀምጦ ተቀመጠ፡፡
‹‹ስምህ ፊራኦል ነው አይደል ምን ማለት ነው?፡፡››
‹‹በትክል የስሙ ትርጉምን ለማወቅ ፈልጋ ሳይሆን እንዲሁ ወደጫወታ እንዴት እንደምትገባ ግራ ስለገባት የሰነዘረችው ጥያቄ ነበር ‹‹ከዘመድ ሁሉ በላይ ነህ..ወይም ከዘመድ ሁሉ በላይ ሁን ማለት መሰለኝ....እኔ ግን ከዘመድ ሁሉ እኩል እንጂ በላይ መሆን አልፈልግም፡፡››
‹‹ሶሻሊስት ነገር ነህ ማለት ነው?››
‹‹በይው..እንዳንቺ አይነት ካፒታሊስት በበዛበት አለም ሶሻሊስት መሆን ከባድ ቢሆንም አዎ ሳሻሊስታዊ ነኝ፡፡››
‹‹እኔ ካፒታሊስታዊ መሆኔን በምን አወቅክ?››
‹‹በወዝሽ››
ከቀናት በኃላ ከት ብላ ሳቀች‹‹እንዴ እንዲህ ቆሳስዬ እና ግማሽ ፊት በባንዴጅ ታሽጎ ወዜን እንዴት ማወቅ ቻልክ?፡፡››
‹‹ወዝሽ  እኮ  ፊትሽ  ላይ  ብቻ  አይደለም  ያለው…የቆዳሽ  ልስላሴ  እኮ  የሰው አይመስልም…ጌጣጌጦችሽም አንዱ ምስክር ናቸው…››
‹‹እንዴ አርቴ እኮ ነው፡››

‹‹አይ ቤተሰቦቼ..ማለቴ እህቴ አርቴ ነው ብላ ስታወራ ሰምቼለሁ....እኔ ግን ስለጌጣጌጥ የተወሰነ እውቀቱ አለኝ …አርቴ እዳልሆኑ እርግጠኛ ነኝ››
‹‹ጎበዝ ነህ!!››
የተወሰነ ደቂቃ በመካከላቸው ፀጥታ ሰፈነ ‹‹ምንድነው የምትሰራው?››ስትል ድንገት ጠየቀችው..ጥያቄዋ እንዲሁ በመሀከላቸው የተጀመረውን ጫወታ ለማራዘም ብላ እንጂ ምንም ይስራ ምንም የሚያስጨንቃት አይነት ሆኖ አይደለም፡፡
‹‹ገንዘብ ያስገኝ እንጂ ያገኘሁትን ሁሉ ሰራለሁ››
‹‹ማለት…?››
‹‹ማለትማ ማርኬቲንግ ነው የተመረቅኩት…ሱፐር ማርኬት ውስጥ ሰርቼ አውቃለሁ…የጅውስ ማከፋፈያ ፋብሪካም ተቀጥሬ ሰርቼ አውቃለው…..ቆርቆሮ ፋብሪካም ሰርቼ ነበር..አሁን ግን አንድ ጌጣጌጥ መሸጫ ሱቅ ውስጥ ነው እየሰራሁ ያለሁት፡፡››ሲል አብራራላት
‹‹አኸ…ስለጌጣጌጤ የተናገርከው ከዛ ልምድ በመነሳት ነዋ››
‹‹ይሆናል››
‹‹ግን ቆርቆሮ ፋብሪካ የትኛው ቆርቆሮ ፋብሪካ ነው የሰራኸው?››
‹‹በፀሎት ቆርቆሮ ፋብሪካ…እዛ ሁለት አመት ሰርቼው›› ከድንጋጤዋ የተነሳ ..ትን አላት…ደንግጦ ተነሳና ጀርባዋን ደገፋት
‹‹ደህና ነኝ ደህና ነኝ››
‹‹ምነው ..ያልሆነ ነገር ተናግሬ አስደነገጥኩሽ እንዴ?››
‹‹አይ በፀሎት የሚባል ቆርቆሮ ፋብሪካ መኖሩን አላውቅም ነበር…››
‹‹እንግዲህ ቆርቆሮን በተመለከተ ምንም እውቀት የለሽም ማለት ነው…..በፀሎት እኮ አገሪቱ ውስጥ ካሉ ትላልቆቹ ቆርቆሮ አማራቾች መካከል አንዱ ነው…ባለቤትነቱ የቢሊዬነሩ ባለሀብት የአቶ ኃይለመለኮት ነው…..በፀሎት የልጃቸው ስም ነው፡፡›

‹‹አይገርምም..የእኔም ስም በፀሎት በመሆኑ እኮ በእኔ ስም የሚጠራ ቆርቆሮ ፋብሪካ ባለማወቄ ተደንቄ ነው...ሰውዬውን ማለቴ ባለቤቱን ታውቃቸዋለህ?››
‹‹አዎ …አውቃቸዋለው…ማለቴ በመጠኑ .. ሁለት ወይም ሶስት ቀን እሷቸውን የማናገር እድል ነበረኝ››
‹‹ልጃቸውንስ?››
‹‹እሷን የፋብሪካው በራፍ ላይ በትልቁ ቢልቦርድ ላይ የተለጠፈው ምስሏ ለአመታት ሳየው ነበር ….ይሄኔ እሷ በስሟ ወላጆቼ ፋብሪካ እንዳላቸው ሁሉ አታውቅም ይሆናል..ግን ይገርምሻል አሁን በጣም ትናፍቀኛለች…ብዙ ቀን ላገኛት ሞክሬ ነበር ግን አውሬ መሳይ ጋርዶቾ ሊያስጠጉኝ አልቻሉም….ግን በቅርብ እንደማገኛትና እንዲህ እንደእኔና እንዳንቺ ፊትለፊት ተቀምጠን ብዙ ብዙ ነገር እንደምናወራ እርግጠኛ ነኝ…በሆነ መንገድ የግድ ማግኘት አለብኝ››
ንግግሩን ስትሰማ በተቀመጠችበት ሰውነቷ ሲንቀጠቀጥና የልብ ምቷ ሲጨምር ታወቃት…
‹‹ትናፍቀኛለች ነው ያልከው…..ግራ አጋቢ ነገር ነው››ይብልጥ እንዲያወራ የሚያበረታታ ዓ.ነገር ጣል አደረገች፡፡
‹‹ግራ አትጋቢ…አብራራልሻለሁ …ቆይ እንደውም…››አለና ኪሱ ገባና የገንዘብ ቦርሳውን አወጣ ….ምን ሊያደርግ ነው ብላ ስትጠብቅ….ከፈተውን አንድ ጉርድ ፎቶ አወጣና አቀበላት…‹‹አየሻት…በፀሎት ማለት ይህቺ ነች…››ብሎ መች እንደተነሳች የማታውቀውን የገዛ ፎቶዋን እጇ ላይ አስቀመጠላት…ለተወሰነ ጊዜ ድንዝዝ አለች፡፡
‹‹ፎቶዬን እንዴት…..?››
‹‹ምን አልሺኝ?››
በመዘባረቋ ደንግጣ‹‹ማለቴ ..የልጅቷን ፎቶ አንተ ጋር ምን ይሰራል….?››
‹‹…ስለምትናፍቀኝ እልኩሽ እኮ…እርግጥ ቀጥታ እሷ አይደለም የምትናፍቀኝ ….እህቴ በሬዱ ነች…አወሳሰብኩብሽ አይደል፡፡ታላቅ እህቴ በሬድ ከሁለት አመት በፊት ነው በአደጋ ምክንያት የሞተችው…ታላቄ ነበረች..የሁለት አመት ታላቄ..የቤቱ እጅግ ተወዳጅ ልጅ ነበረች….ባንክ   ነበር   የምትሰራው…የቤታችንን   ወጪ   ግማሹን   እሷ   ነበረች

የምትሸፍነው…ግን ድንገተኛ የመኪና አደጋ ደረሰባትና ሆስፒታል ገባች፣የዛን ጊዜ እኔ የነበፀሎት ቆርቆሮ ፋብሪካ ነበር የምሰራው….እና እህቴ ክሪትካል ኬዝ ላይ ደረሰችና ጭንቅላቷ በጣም ተጎድቷ ስለነበረ ወደውጭ ሄዳ ብትታከም ጥሩ እንደሆነ ሀኪሞቹ ምክር ሰጡ ..እኛ አቅማችን አይችልም ነበር…በአጋጣሚ በዛን ጊዜ በፀሎት የልብ በሽታዋ ከፍተኛ ደረጃ ደርሶ ወደውጭ ለህክምና ለመሄድ ዝግጅት ላይ ነበረች…እኔ እህቴን ለማሳከሚያ የእርዳታ ብር ለመሰብሰብ እላይ እታች በመሯሯጥ ላይ ነበርኩ ….ከመስሪያ ቤት ሰራተኞች እየተሰበሰበ ሳለ አቶ ኃይለመለኮት ድንገት ፋብሪካውን ለመጎብኘት ይመጣሉ..እና እያለቀስኩ እርዳታ ከሰራተኞች ስሰበስብ አይተውኝ ወደመኪናቸው ይዘውኝ ገቡና ምን እንደሆንኩ ጠየቁኝ…እያለቀስኩ በቤተሰባችን የደረሰውን መከራ ነገርኮቸው………
‹‹በቃ እርዳታ መሰብሰቡን አቁም እኔ እህትህን አሳክምልሀለው››አሉኝ በፍፅም እውነት አልመሰለኝም ነበር…ግን ከምራቸው ነበር..‹‹ከአስር ቀን በኃላ ልጄን ለልብ ህክምና ወደታይላንድ ይዤት ስለምሄድ እህትህንም እዛ ሔዳ መታከም ትችላለች..የህክምና ማስረጃውን ጨርሱ የጉዞ ሰነድችን የእኔ ሰዎች ያመቻቻሉ››ብለው አስፈነጠዙኝ፡፡
ቃላቸውን ጠብቀው እህቴን ከአባቴ እና ከገዛ ልጃቸው ጋር ይዘው ታይላንድ ሄዱ…እህቴ ታይላንድ በገባች በአስራ ሶስተኛው ቀን ህይወቷ አረፈ….….በዛን ጊዜ ደግሞ በተመሳሳይ ቀን የፀሎት ልቧ ፌል አድርጎ በህይትና በሞት መካከል ስታጣጥር ነበረ…ብቻ ፕሮሰሱ ብዙ ነው…በስተመጨረሻ አባቴ ልጄ ሙሉ በሙሉ እንዳትሞት ልቧን መለገስ እፈልጋለው አለና ፍቃደኛ ሆኖ እዛው የእህቴ የበሬድ ልብ ለበፀሎት ተገጠመላትና..አባቴ የእህቴን ሬሳ ጭኖ መጣ እልሻለው፡፡፡››
‹‹በጣም የሚገርም ልብ ሰባሪ ታሪክ ነው የነገርከኝ››
‹‹አዎ በጣም ልብ ሰባሪ ነው…አይገርምም የአንዱ ቤት ደስታ በሌላው ቤት ሀዘን ላይ መብቀሉ…አንዱ እንዲስቅ ሌላው ማልቀስ አለበት…ህይወት እንዲህ ኢፍትሀዊ መሆኗን ከዛ በፊት አላውቅም ነበር››
‹‹በቃ አትበሳጭ ..እናውራ ብዬ ..አስደበርኩህ አይደል?››
‹‹አረ በፍጽም..››ብሎ ሊያብራራት ሲል የሰርቢሱ በራፍ ተከፈተ… ሁለቱ ፊታቸውን ሲያዞር አቶ ለሜቻ ነበሩ፡፡

‹‹እንዴ ልጄ አመመሽ እንዴ… ?ፊራኦል ለምን ሳትቀሰቀኝ?››ልጃቸውን ተቆጡት
‹‹አይ አባዬ …አላመማትም..እንቅልፍ እምቢ ሳላላትና እቤቱ ስለሞቃት ነው ውጭ የወጣነው፡፡››
‹‹አዎ አበባ ..ደህና ነኝ…እንቅልፍ እምቢ ስላለኝ ነው፡፡››እንዳላመማት አረጋገጠችላቸው፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

23 Dec, 20:09


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ስድስት

ማታ አንድ ሰዓት የቤቱ ሰው ሁሉ ተሰብስቦ ጠባቧን ሳሎን ሞሏት…መጨረሻ ላይ የመጣው ፊራኦል ነበር…በእጁ አንድ ኪሎ ሙዝ ይዞ ነበር፡፡
ለሊሴ ከተቀመጠችበት ተስፈንጥራ ተነስታ ከእጁ መንጭቃ ተቀበለችው እና‹‹..ወንድሜ ሙዝ ገዛኸልኝ….!!! ደሞዝ ደረሰ እንዴ?››ስትል በፈገግታ ተሞልታ ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ እንደምታውቂው ቀኑ ገና 18 ነው….በ18 ደግሞ ደሞዝ የለም…ስለዚህ ሙዙ ላንቺ አይደለም››ሲል መለሰላት፡፡
ለሊሴ ግራ ገብቷት‹‹ እና››ስትል አይኖቾን በማፍጠጥ ጠየቀችው፡፡
‹‹ለበሽተኛዋ ማለቴ… ለእንግዳዋ ነው››ሲል ያልጠበቀችውን መልስ ሰጣት፡፡
‹‹እ ነው…እሺ…››አለችና ፔስታሉን ወደበፀሎት ወስዳ ስሯ አስቀመጠችላት…፡፡

በሳቅና በጫወታ በደመቀ ምሽታ እራት ተበላ… ቡና ተፈልቶ ተጠጣ….ከጓዲያ የተጠቀለለ የጥጥ ፍራሽ ወጣና ወንበሮቹ ተሰብስበው ከእሷ ጎን ተነጠፈ…ለሊሴ ከጎኗ በተነጠፈው የጥጥ ፍራሽ ላይ ስትተኛ ፊራኦል ደግሞ ከእነሱ ራቅ ብሎ ግድግዳውን ተደግፎ ካለ አሮጌ ሶፋ ላይ አንድ አልጋ ልብስ ተከናንቦ ተኛ…
‹‹ለሊሴ ታዲያ ስትበራገጂ እግሯን እንድትነኪባት››
‹‹አረ አታስቢ እማዬ …እጠነቀቃለሁ፡፡››
ለሊሴ በፀሎትን ‹‹ለሊት የሆነ ነገር ከፈለግሽ ቀስቅሺኝ››አለችትና የለበሰችውን አልጋ ልብስ ተከናነበች፡፡
‹‹እሺ ቀሰቅስሻለሁ..ደህና እደሩ ››ስትል መለሰች፡፡
‹‹ደህና እደሪ….ወንድሜ ደህና እደር››
‹‹ምኑን ደህና አደርኩት ….ዛሬ ደግሞ ምን አልባት ሴኖ ትራክ ይሆናል ቤታችን ላይ የሚወጣው…. ››
‹‹ወንድሜ ደግሞ.. አሽሙራም ነገር ነህ››
‹‹እሺ መብራቱን ላጥፋው?››ፊራኦል ጠየቀ፡፡
‹‹አጥፋው››በፀሎት መለሰች፡፡
መብራቱ ጠፋ፡፡ ፀጥታ ሰፈነ፡፡ ሁሉም ፀጥ ያለና በእንቅልፍ የተዋጠ ይመስል ነበር..በፀሎት ግን ፈፅሞ እንቅልፍ ሊወስዳት አልቻለም...ጨለማው ውስጥ አይኗን አፍጥጣ በጭንቀት እያሰላሰለች ነበር..ይሄኔ የአባቷ ቅጥረኞች ድፍን አዲስ አበባን እየገለባበጦት እንደሚሆን እርግጠኛ ነች..
‹‹የፈለገ ቢገለባብጡ የፈለገ ያህል ቢሞክሩ አያገኙኝም….››ስትል እርግጠኛ ሆነች፡፡ስልኳን ከቤት ይዛ አለመውጣቷ አሁን ነው ያስደሰታት….እንደዛ ባታደርግ ኖሮ ያንን ተከትለው ያለችበትን ለማግኘት ይሞክሩ ነበር አሁን ግ ምንም እድል የላቸውም…አዎ አሁን ባልና ሚስቶቹ እየተናቆሩም ቢሆን እሷን በመፈለጉ አንድ ላይ ለማውራትና ለመተባበር ይገደዳሉ…ምን  አልትም  ወደቀልባቸው  እንዲመለሱ  ምክንያት  ሊሆናቸው  ይችል

ይሆናል…ይሄ የእሷ ምኞት ነው፡፡ካለበለዚያም ይለይላቸውና እርስ በርስ ይገዳደሉ ይሆናል፡፡‹‹እንደዛ ከሆነ እስከወዲያኛው እገላገላቸዋለው››አለችና በረጅሙ ተነፈሰች፡፡ እንዲሁ ስትገላበጥና ስትተክዝ እኩለ ለሊት ሆነ፡፡ በአእምሮዋ የሚጉላላው ሀሳብ ብቻ አይደለም እቅልፍ የነሳት… የእግሯም ጥዝጣዜ ጭምር ነው ፡፡በዛ ላይ ሽንቷን ወጥሯታል….‹‹እንዴት ነው የማደርገው.?››ስትል እራሷን ጠየቀች፡፡.እንደምንም ተቆጣጥራው እስከንጊት ለማቆየት ብትጥርም አልቻለችም..አምልጧት ከመዋረዷ በፊት ከጎኗ ድብን ያለ እንቅል የተኛችውን ሊሊሴን መጣራት ጀመረች‹፡፡
‹‹ሌሊሴ….ሌሊሴ››
ያልጠበቀችው ሻካራ ድምጽ መልስ ሰጣት..‹‹አትልፊ እህቴን እንኳን በጥሪ በመድፍም ልትቀሰቅሻት አትችይም››
ግራ ተጋብታ ምን እንደምትመልስ እያሰላሰለች ሳለ መብርቱ በራ…በቁምጣና በጃፖኒ ቲሸርት ውጥርጥር ያለ ሰውነቱን በከፊል አጋልጦ ካለችበት በሶስት እርምጃ ርቀት ቆሟል…
‹‹ምን ልስጥሽ?››ሲል ጠየቃት
‹‹አይ..ሽንት ቤት መሄድ ፈልጌ ነበር››ፈራ ተባ እያለች መለሰችለት፡፡
‹‹ምን ፖፖ ላምጣልሽ?››
ፖፖ ቢያመጣላት እዚህ እፍንፍን ያለ ቤት ይሄ ሁሉ ሰው ባለበት እንዴት አድርጋ እንደምትሸና አሰበችና‹‹ አይ ሽንት ቤት ነው መሄድ የፈለኩት››በማለት መለሰችለት፡፡
‹‹እንግዲያው እሺ›› አለና ወደበራፍ በመሄድ የተቀረቀረውን በራፍ ወለል አድርጎ ከፈተና ተመልሶ ወደእሷ መጣ …ምን ሊያደርግ ነው ብላ አፍጥጣ እያየችው ሳለ በርከክ ብሎ ስሯ ተቀመጠና የለበሰችውን ብርድ ልብስ ከላዮ ላይ ገፈፈ፡፡ እጆችን በትከሻዋና በእጆቾ መካከል አሰቅስቆ አስገባ..
‹‹ምን እያደረክ ነው?››ግራ በተጋባ ድምፅ ጠየቀችው፡፡
‹‹መቼስ እንዲህ ተሰባብረሽ ልራመድ አትይም….እንደፈረደብኝ አቅፌ ሽንት ቤት እየወሰድኩሽ ነው››

‹‹አረ ተው ..እነጋሼ ብያዩን ምን ይሉናል?››
‹‹አይዞሽ እነጋሼ ልጃቸው ምን አይነት ልጅ እንደሆነና እንዴት አድርገው እንዳሳደጉት ስለሚያውቁ ምንም አይሉም…..ምን አልባት ግን ይመርቁኝ ይሆናል››አለና አንከብክቦ አቅፎ ከቤት ይዟት ወጣ፡፡የልጁ ድርጊት ፍጽም ያልጠበቀችው ስለሆን በጣም ነው የተደመመችው፡፡እንደተሸከማት ከሰርቢስ ቤቱ ጫፍ በኩል ክፍቱን ካለ አንድ ክፍል ወስዶ ወደውስጥ ደፉን አሳለፈና ደግፎ አቆማት…ከዛ ቀኝ እጁን ዘረጋና በቀይ የኤሌክትርክ ገመድ ጫፍ ላይ የተንጠለጠለውን ማብሪያ ማጥፊያ ሲጫናው የሽንት ቤቱ መብራት ቦግ ብሎ በራና በክፍሉና በአካባቢው ያለው እይታ ወለል ብሎ አንዲታየ አደረገ …
ደረቱ ላይ ተደግፋ እንደቆመች ሽንት ቤቱን ቃኘችው..ስፋቱ ሁለት ካሬ እንኳን አይሞላም
…በዛ ላይ ከለመደችው አይነት መፀዳጃ ቤት ፍፅም የተለየና የማይነፃፀር አይነት ነው….ይህን መሰል አይነት ሽንት ቤት በምስል አንኳን አይታው የማታውቀው አይነት ነው፡፡እርግጥ ፅዳቱ የተጠበቀ በመሆን ዝግንን የሚል የመቅፈፍ አይነት ስሜት እንዲሰማት የሚያደርግ አይነት አይደለም…ቢሆንም በምቾት ዘና ብላ የምትቀመጥበት አይነት አይደለም…‹‹በቃ እንደምንም ግድግዳውን ተደግፈሽ ቁሚ..››ትዕዛዙን ስትሰማ እንደምንም የተበታተነ ሀሳቧን ሰበሰበች፡፡
እስከአሁን ደረቱን ተደግፋ መቆሟን ትዝ ሲላት እንደመደንገጥ አለችና ግራና ቀኝ እጇን የሽንት ቤቱን በራፍ ግራና ቀኝ ጉበን ይዛ ቆመች…ትቷት ወደኃላ ሸሸና መራመድ ሲጀምር
በመደንገጥና በመገረም ስሜት‹‹እንዴ? ጥለኸኝ ልትሄድ እንዳይሆን?››ስትል ጠየቀችው፡፡
እርምጃውን ሳያቋርጥ ‹‹መጣሁ..››አለና ከበራፉ አካባቢ አንድ ባዶ ሀይላንድ ላስቲክ ይዞ ወደ ቧንቧው በመሄድ ውሀ ቀድቶ ከሞላበት በኃላ ..ወደእሷ ተመለሰና እጁን አንጠራርቶ ከሽንት ቤቱ ቀዳዳ አጠገብ አስቀመጠላትና …‹‹..ግቢና እንደምንም ተቀመጪ››አላት፡፡
ወደውስጥ ዘልቃ ገባች‹‹በራፍ የለውም እንዴ?››ሌላ ያስጨነቃትን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡
‹‹አይዞሽ….ምንም አትሆኚም››አለና ወደላይ ተሰብስቦ የተጠቀለለ ጨርቅ ነገር አላቀቀና እንደመጋራጃ ወደታች ለቆ ጋረደላት…..የእግሯን ጥዝጣዞ እንደምንም ችላ በአንድ አይኗ አጨንቁራ በማየትና ነገሮችን በመቆጣጠር እደምንም ተቀምጣ ለመተንፈስ ቻለች..ጨርሳ ስትወጣ ተንደርድሮ ከበራፍ ተቀበላትን ሰቅስቆ አቀፋት፡፡

‹‹ካላስቸገርኩህ ጨረቃዋ ደስ ትላለች ..ትንሽ ውጭ መቀመጥ እንችላለን?››ስትል በልመና ቃና ጠየቀችው፡፡
‹‹እንደፈለግሽ.. ››አለና ግድግዳውን አስደግፎ አቆማትና ትቷት ወደውስጥ ሊገባ መራመድ ጀመረ…

ከመጽሐፍት መንደር💠

21 Dec, 17:45


ወ.ሮ እልፍነሽ ጥያቄው መደናገር ውስጥ አስገባቸው‹‹ለምን ጠየቁኝ?››
‹‹አይ እንዲሁ ነው..ይህቺ የወንድሙ ልጅ እጅግ የሀብታም ልጅ እንደሆነች ያስታውቃል››
‹‹እንዴት ነው ሚያስታውቀው…?ያደረገችውን ልብስና የደረገችውን አርቴፊሻል ጌጥ ተመልክተው ነው?››
‹‹አይ ፍፅም እነሱን አይቼ አይደለም…ሰውነቷን አይቼ ነው…ልስላሴው እኮ ከሀር ጨርቅ በላይ ነው…..እጅግ ቅንጡ አስተዳደግ ያደገች የንጉስ ልጅ ነው የምትመስለው…አዎ በደንብ ያስታውቃል፡፡››አሉ እርግጠኛ በመሆን፡፡
ወ.ሮ እልፍነሽ‹‹ይሆናል››ብለው በድፍኑ መልስ ሰጡ፡፡

‹‹እንግዲ..ከሶስት ቀን በኃላ መጥቼ አያታለው…ሾርባ ነገር እያደረጋችሁ በደንብ ተንከባከቧት …ትድናለች……በሉ›› ብለው ሲወጡ አቶ ለሜቻ ወደውስጥ ገቡና ወደባለቤታቸው በመቅረብ….‹‹የእኔ አለም….ለውጌሻዋ የሚከፈል ብር አለሽ አንዴ?››ሲሉ ልብን በሚሰረስር ትህትና ጠየቁ፡፡
‹‹ስንት ይሆን….?››
‹‹ሁለት መቶ ብር ነው..እኔ ጋር መቶ ብር አለ፡፡››
በፀሎት በወገባቸው ዙሪያ የተጠመጠመ መቀነታቸውን ሲፈቱ አጨንቁራ እያየቻቸው ነው..ከቋጠሮ ውስጥ ድፍን ሁለት መቶ ብር አወጡና ለባለቤታቸው ሰጦቸው….
‹‹መቶ ብሩን አትሰጪኝም…?››
‹‹ኪስህማ ባዶ መሆን የለበትም…ግድ የለህም ሂድ ውጌሻዋን ሸኛት ››
አቶ ለሜቻ የተሰጣቸውን ብር በእጃቸው እያሻሹ ወደ ውጭ ወጡ…ወ/ሮ እልፍነሽ ወደጓዲያ ገብና በጓድጓዳ ሰሀን ምግብ እና በብርጭቆ ውሀ ይዘው በመምጣት ስሯ ቁጭ አሉ ፡፡
የተኛች መስሎቸው ቀስ ብለው ትከሻዋን ያዙና ‹‹የእኔ ልጅ ..የእኔ ልጅ››ሲሉ ሊቀሰቅሷት ሞከሩ… ቀስ ብላ አይኗን ስትገልጥ እንጀራ የጠቀለለ እጃቸው አፏ አካባቢ ደርሶል….‹‹በ…ቃኝ…እማ….ማ››
‹‹አይ….በቃኝ አይሰራም…ካልበለሽ አትድኚም…እንደምንም ባይጣፍጥሽም ታግለሽ መብላት አለብሽ››ኮስተር አሉባት፡፡
አሳዘኗት…‹‹ቆይ ማንነቴን አያውቁ ለምንድነው እንዲህ እየረዱኝ ያሉት….?ነው ወይስ የልጃቸውን ልብ የተሸከምኩ መሆኔን ደመነፍሳቸው ነግሯቸው ይሆን?››መልስ በቀላሉ ልታገኝለት ያልቻለችው ጥያቄ እራሷን ጠየቀች፡፡
ለእሳቸው ስትል እንደምንም አፏ ከፈተች…አፏ ውስጥ ከተቱት…በመከራ አላመጠችና ዋጠች..እንቁላል ፍርፍር ነው…በመከራ አምስት ጉርሻ ያህል አጎረሶትና ወደላይ ደግፈው ውሀ እንድትጠጣ ካደረጉ በኃላ አስተኟት…፡፡ከዛ አቶ ለሜቻም ውጌሻዋን ሸኝተው ስለተመለሱ ለቤተሰቡ ጠቅላላ ቁርስ ቀረበና ተሰብስበው እየተጎራረሱ  ሲበሉ አየች….ያ

ደግሞ ይበልጥ ስለወላጆቾ ቤት እንድታስብና ልቧ እንዲሰበር አደረገ ..ለእሷ እንቁልል ጠብሰው ያባሏት ሴትዬ ለቤተሰቡ ደረቅ ዳቦ በሻይ ነው ማቅረብ የቻሉት፡፡የገረማት ደግሞ እሱንም በፍቅር እየተሳሳቁ ይጎራረሳሉ፡፡
እሷ ቤት በየቀኑ ጠረጴዛ ሙሉ ለአይን እራሱ የሚያታክት ምግብ ይቀርባል፡፡ የሚበላው ግን አስር ፐርሰንትም አይሞላም…ከዛ የተረፈው ምን እንደሚደረግ አታውቅም..ምን አልባት እዛ ጊቢ ውስጥ ለሚሰሩ ሰራተኞች ይታደል ይሆናል… ወይም ደግሞ ተበላሽቶ ገንዳ ውስጥ ሊደፋም ይችል ይሆናል…..እዚህ ግን እቤቱ ያፈራውን ምርጥ ምግብ ለማያውቁት እንግዳ ሰው አብልተው እነሱ ደረቅ ዳቦ ይቆረጥማሉ..ለዛውም በጫወታ የደመቀ በደስታ የታጀበ ቁርስ ነው እየበሉ ያሉት…እነሱ ቤት ግን በኩርፊያ የታጀበ ቁርስ ነው የሚሆነው..ወሬ ካለውም በአሽሙርና በነቆራ የታጀበ በሚያስጠላ ጥል የሚገባደድ ነው የሚሆነው፡፡
ይበልጥ ሆድ ባሳት….‹‹በምንም አይነት ወደእዛ ቤት በቀላሉ አልመለስም››ለራሷ ዳግመኛ ቃል ገባችና አይኗን ጨፈነች..ደክሞት ስለነበረ ወዲያው ነበር ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰዳት፡፡
‹‹የእኔ ልጅ ተነሽ….›› የሚል ድምጽ ነበር ከእንቅልፏ ያባነናት..ምን ያህል እንደተኛች አታውቅም፡፡ ብቻ አይኖቾን ስትገልጥ ልክ እንደቅዱሙ ያች ደግ እናት ምግብ በሰሀን ይዛ ልክ እንደህፃን ልጅ ልታጎርሳት ስሯ ቁጭ ብላለች፡፡
‹‹እማማ…አራበኝም እኮ ..አሁን አይደል እንዴ የበላሁት?››
‹‹አይ አሁን እኮ ሰባት ሰዓት ሆኗል…አባትሽ ላንቺ ሲል ነው ስጋ ገዝቶ የመጣው… እኔ እናትሽ ደግሞ ቆንጆ አድርጌ ሰርቼሻለሁ››
‹‹በሰማችው ነገር አንባዋ በአይኗ ግጥም አለ….››
‹‹ነይ እስኪ ለሊሴ ትንሽ ቀና ትበል ትራስ ደርቢላት›ለሊሴ መጣችና ደግፋ ቀና አድርጋ ትራስ ደረበችላትና ወደቦታዋ ተመለሰች …ቡና እያፈላች ነው..አቶ ለሜቻ ከለሊሴ ፊት ለፊት ባለ ደረቅ ወንበር ላይ ቁጭ ብለው በፀጥታ እየተመለከቷት ነው፡፡
‹‹እንጀራውን ጠቅልለው ወደ አፏ ዘረጉት…አፏን ከፍታ ተቀበለቻቸው…አላምጣ ከወጣች በኃላ…

‹‹እናንተስ አትበሉም?››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹አዬ ልጄ …አኛማ በልተን ጨርሰን ቡና ስንጠብቅ አታይንም..አንቺ ብይ››አቶ ለሜቻ መለሱላት፡፡ወይዘሮ እልፍነሽ አብልተዋት ከጨረሱ በኃላ አቶ ለሜቻ ከተቀመጡበት ተነስተው ወደእሷ ተጠጉና ፍራሹ ጫፍ ላይ ተቀመጡ…የሆነ ነገር ሊጠይቋት እንደሆነ ገብቷት ዝግጁ ሆነች፡፡
‹‹ስምሽ ማነው ልጄ?››እስከአሁን ስሟን እና ማንናቷን እንኳን ሳያውቁ ይሄን ሁሉ እገዛና እንክብካቤ ሲያደርጉላት እንደቆዩ ስታስተውል ግርም አላት፡፡‹‹በፀሎት እባላለሁ››
‹‹እኔ አባትሽ..ለሜቻ እባላለሁ..እናትሽ ደግሞ እልፍነሽ ነው ስሟ….የመጀመሪያ ወንዱ ልጄ ፍራኦል..እሷ ደግሞ የእሱ ተከታይ ለሊሴ ትባላለች..፡፡››የቤተሰቡን አባላት ሁሉ በስማቸው እየጠሩ አንድ በአንድ አስተዋወቋት…በፅሞና እያዳመጠቻቸው መሆኑን ከተገነዘቡ በኃላ ንግግራቸውን አራዘሙ‹‹በእውነት በዛ ውድቅት ለሊት በዛ ሞተር ሆነሽ ከቤታችን ጋር ተጋጭተሸ ስትወድቂ በህይወት የምትተርፊ መስሎ አልተሰማኝም ነበር… ሁላችንም በጣም ፈርተን ነበር..ግን አምላክ ደግ ነው እና አጋልጦ አልሰጠንም…ተርፈሻል….ይመስገነው››
አሁን እሷቸው ሲናገሩ ሞተሩና ቦርሳዋ ትዝ አላት….ሞተሩ ምንም ቢሆን ግድ የላትም ቦርሳዋ ግን ያስፈልጋታል…
‹‹ወይኔ አባባ የሆነ ቦርሳ ይዤ ነበር …ጣልኩት እንዴ?››እሰከዛን ሰዓት ድረስ እንዴት ትዝ እንዳላላት ለራሷም ገረማት.፡፡፡
‹‹…አይ ልጄ አልጣልሺውም… ቦርሳውም ሞተሩም ጓዲያ ተቀምጦልሻል…ሞተሩን ወደውስጥ ያስገባነው ምን አልባት ችግር ላይ ሆነሽ ከፖሊስ እየሸሸሽ ወይም ከሆነ ሰው እየተደበቅሽ ከሆነ እንዳትጋለጪ ብለን ነው…››
‹‹አይ አባባ…እምልሎታለው የነገርኳችሁ እውነቴን ነው..ከፖሊስ ጋር የሚያገኛኘኝ ምን ነገር የለም…ከእንጀራ አባቴ ጋር ተጣልቼ ነበር …በለሊት ከቤት ወጥቼ በንዴት ስነዳ የነበረው››
‹‹አዎ እኔም ጠርጥሬለው…የቤተሰብ ችግር እንደሆነ ታውቆኝ ነበር››

‹‹ውይ ልጄ ይሄኔ እናትሽ በጭንቀት ልትፈነዳ ደርሳለች››ወ.ዘሮ እልፍነሽ በእናትነት አንጀታቸው የተሰማቸውን ተናገሩ ….ስለራሳቸው ልጆች እያሰቡ ስለነበር ነው ስሜቱ የተጋባባቸው፡፡
በፀሎት‹‹አይ እናቴ አትጨነቅም››ፍርጥም ብላ መለሰች፡፡
‹‹ምን ማለትሽ ነው ልጄ …?በጣም ነው እንጂ የምትጨነቀው..እናንተ ልጆች የእናትን አንጀት እስክትወልዱ ድረስ አይገባችሁም…ይሄኔ በየፖሊስ ጣቢያው እና በየሆስፒታሉ አንቺን ፍለጋ እየተንከራተተች ነው፡፡››ወ.ሮ እልፍነሽ ጠንካራ እምነታቸውን በድጋሜ ገለፁ፡፡
‹‹እይ እደዛ ማለቴ አይደለም ..እናቴ ከሁለት ወር በፊት ነው የሞተችው›››
‹‹ውይ ታዲያ እንጀራ አባትሽ እናት የሞተባትን ልጅ ምን አድርጊ ነው የሚልሽ….?ሌሎች እህትና ወንድም የለሽም›?›
‹‹የለኝም እኔ ብቻ ነኝ››
‹‹ታዲያ በውድቅት ለሊት ምን አጣላችሁ?››

ከመጽሐፍት መንደር💠

21 Dec, 17:45


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አምስት


ከጥዋቱ ሁለት ሰዓት ለመጀመሪያ ጊዜ የቀኝ እጇ የመሀል ጣት ተነቃነቀ…እቤቱ ውስጥ ያለው ሰው ሁሉ በደስታ ፈገገ ..ከአስር ደቂቃ በኃላ አይኖቾ ተከፈቱ፣አራቱም የቤቱ አባላት የተኛችበትን ፍራሽ በሁሉም አቅጣጫ ከበው በፈገግታ ያዩት ጀመር….ግራ ገባት፡፡መልሳ አይኖቾን ጨፈነች…፡፡መንቃቷ እራሱ የእውነት ሳይሆን በህልም አለም ውስጥ የተፈጠረ መንቃት ነው የመሰላት ፡፡ለዛ ነው ዳግመኛ እይኖቾን የጨፈነችው..፡፡መልሳ ስትገልጥ ያየችው ተመሳሳይ ነገር ነው….አራት ወዛቸው የተመጠጠ የለበሱት ልብስ የነታተበ ..በአባቷ ግቢ ውስጥ አትክልቶችን ከሚንከባከቡ ሰራተኞች በላይ ኑሮ የጠበሳቸው ጠና ያሉ ሰውዬ…ቆዳቸው የተሸበሸበ እናት… የ ሀያ አመት ልጅ እግር የምታምር ግን ደግሞ ያልተመቻት ልጃገረዶች..ባለጡንቻ ፈርጣማ እና ባለኮስታራ ፊት ሀያ አምስት ወይም ስድስት የሚሆነው ወጣት ..ጭስ የጠጣና ያረጀ የማዳበሩያ ኮርኒስ ያለው ጠባብ ክፍል…መሬት ላይ የተነጠፈ ፍራሽና ያረጀ በህይወቷ እንኳን ለብሳው አይታው የማታውቀው አይነት ብርድ ልብስ ለብሳ ነበር እራሷን ያገኘችው፡፡ግን እንደዛም ሆኖ የተለየ እና የማታውቀው ቦታ ያለች መስሎ አልተሰማትም….የሆነ ከዘመናት በፊት ታውቀው የነበረ እና ስትናፍቀው የቆየችው ቦታ ተመልሳ እንደመጣች አይነት ስሜት ነው እየተሰማት ያለው
‹‹…የት ነኝ?››
‹‹ልጄ…አሁን ሰላም ነሽ …ትንሽ አደጋ ደርሶብሽ ነው?››
‹‹የምን አደጋ?››
‹‹አሁን ሰላም ነሽ..በውድቅት ለሊት ሞተር ስትነጂ ነበር…ተገልብጠሸ ነው፡፡››
‹‹ሞተር››

‹‹አዎ..ሞተር..ከማን ስትሸሺ ነበር….?እስከአሁን ለፖሊስ አላሳወቅንም…..ይሄውልሽ እኔና ቤተሰቦቼ በህይወት ፈተና ጋር ግብግብ ገጥመን በትግል የምንኖር ሰዎች ነን…ከሆነ ወንጀል ጋር የተያያዘ ታሪክ ካለሽ እባክሽ.እኛንም ጣጣ ውስጥ እንዳንገባ ከአሁኑ ንገሪን››ሲል ፊራኦል ተናገረ፡፡
‹‹ምነካህ ልጄ? ልጅቷ ገና አሁን መንቃቷ ነው…ተው እንጂ ነውር ነው›እናትዬው ገሰፁት..አባትዬውም ለባለቤታቸው ድጋፍ በመስጠት‹‹ልጄ አዎ..አሁን ዋናው ያንቺ መትረፍ ነው ፡፡ሌላውን ቀላል ነው…የሰው ልጅ በህይወት ካለ የማያልፈው መከራ የማያሸነፍው የህይወት ትግል የለም..አሁን አንቺ ምንም አታስቢ..እኔነኝ የተባለ ውጌሻ ጠርቼያለሁ፡፡ ወለምታ ወይም ስብራት ነገር ካለሽ ያዩልሻል…ከዛ ካገገምሽ በኃላ ለቤተሰቦችሽ እንደውልላቸውና መጥተው ይወስዱሻል››
በፀሎት ለሊት በውድቅት ለሊት ከቤቷ አምልጣ እንዴት እንደወጣችና ምን እንዳደረገችና አሁን ያለችበት ቤትም የእነማን እንደሆነ ትዝ እያላት ሲመጣ ….የመረጋገትና የደስታ ስሜት ተሰማት‹‹አመሰግናለሁ…ምንም ወንጀል አልሰራሁም….ፖሊስም እየፈለገኝ አይደለም…አሁን ደክሞኛል ልተኛ..››አለችና መልሳ አይኖቾን ጨፈነች፡፡
‹‹ሰማችሁ አይደል..ምንም ወንጀል አልሰራሁም ብላለች..አሁን ዞር በሉላት …ትንፋሻችሁ እራሱ በሽታ ነው የሚሆናባት››አባትዬው ተቆጡ፡፡
‹‹አባዬ ደግሞ ፣አንተ ሁል ጊዜ ሰው እንዳመንክ ነው.. ሚገርመው ደግሞ ሰዎች ቃላቸውን እያጠፉ አንተን ማሳዘናቸውን አያቆሙም… አንተም ደግሞ ደግመህ አደጋግመህ እነሱን ማመንህን አታቆምም››ፊራኦል ተነጫነጨ፡፡
‹‹ልጄ ገለባ ቢዘሩት አይበቅልም ተጠራጣሪ ሰው አይፀድቅም ይባላል..ያገኘሁትን ሰው ሁሉ በመጠራጠር ህይወቴን ሳሰቃይ ከመኖር እያመንኩ ብከዳ ይሻለኛል…ቢያንስ በማመኔ ምክንያት የሚደርስብኝ ችግር ምክንያቱ እኔ አይደለሁም..››
ፊራኦል በወላጆቹ ውሳኔ ባለመስማማት ‹‹በሉ እሺ እኔ ወደ ስራ ሄጃለሁ፡፡››በማለት ቤተሰቡን ተሰናብቶ ግቢውን ለቆ ሲወጣ በራፍ ላይ ውጌሻዋ ወደውስጥ ስትገባ ተላለፉ፡፡
‹‹ቤቶች አቶ ለሜቻ››ሁሉም ግር ብለው ወጥተው ውጌሻዋን ተቀበሉና ወደውስጥ አስገቧት፡፡

‹‹የትኛው ልጅህ ነች… ለሜቻ?››
‹‹የወንድሜ ልጅ ነች ከድሬደዋ ልትጠይቀኝ መጥታ ነው››
‹‹እና ምን ገጥሟት ነው?››
‹‹ባኮት ከሆነ የሰፈር ልጅ ጋር ሞተር ተፈናጣ ስትሄድ ሞተሩ ተገለበጠባቸውና ትንሽ ተጎዳች..ምን አልባት ስብራት ወይም ወለምታ ይኖራት እንደሆነ ብለን ስለተጠራጠርን ነው ያስቸገርኖት፡፡››
በፀሎት የሚነጋገሩትን ሁሉ አይኖቾን ጨፍና እየሰማች ነው…
‹‹ታዲያ ተኝታለች?››
‹‹አሁን ነቅታ ነበር…እንዴት ነው እንቀስቅሳት?››ወ.ሮ እልፍነሽ ጠየቁ፡፡
‹‹አይ ቆይ ተዋት ..ህመሙ እራሱ ይቀሰቅሳታል፡፡››አሉና ስሯ ፍራሽ ላይ ተቀመጡ…
‹‹ እስቲ እሱን የከሰል ፍም አቅርቡልኝ››ትዕዛዝ ሰጡ፡፡
ማንደጃው ቀረበላቸው…‹‹ እስኪ አንዳችሁ ኑና የለበሰችውን ልብሷን አውልቁላት…..››ለሊሴ ፈጠን ብላ መጣችና ከላይ የለበሳቸውን ጃኬት… ቦዲ ተራ በተራ አወለቀችላት… በጡት ማስያዣ ብቻ አስቀረቻት ፡፡አንገቷ ላይ ያለው የእጅ መዳፍ የሚያህል አብረቅራቂ እንቁ ፈርጥ ያለበት ጌጥ የሁሉንም አይን በቅፅበት ተቆጣጠረ
….ጆሮዋ ላይም ያንጠለጠለችው የጆሮ ጌጥ ከአንገት ሀብሏ ጋር እንዲናበብ ተደርጎ የተሰራ ለልደት በዓሏ ከአባቷ የተበረከተላት ልዩ አይነት ጌጥ ስለሆን በተለይ የሌሊሳን ትኩረት በደንብ ነው የተቆጣጠረው…ሁሉም ግን አርቴ እንጂ ትክክለኛ ነው ብለው አላሰቡም ነበር፡፡
ውጌሻዋ ቦርሳቸው ውስጥ እጃቸውን ሰደዱና በብልቃጥ ከለጋ ቅቤ ጋር ተለውሶ የተዘጋጀ መዳህኒታቸውን አወጡና ፊት ለፊታቸው አስቀምጠው በሌባ ጣታቸው ዛቅ እያደረጉና በመሀል አጣታቸው ላይ አድርገው በመላ መዳፋቸው ላይ ለቀለቁና ስራቸው በቀረበላቸው የከስል ፍም ላይ ጠጋ አድርገው ሙቀት እንዲያገኝ ካደረጉ በኃላ ከአንገቷ ጀምሮ ትከሻዋን እያሹ መፈተሽ ጀመሩ‹‹ ..ምንም አልሆነችም እስኪ ሱሪዋን አውልቁልኝ››ሌላ ትዕዛዝ ሰጡ..በዚህ ጊዜ አቶ ለሜቻ ከተቀመጡበት ተነሱና ወደውጭ ወጡ..ሴቶቹ እንደምንም

ታጋግዘው የለበሰችውን ጅንስ ሱሪ ከላዮ ላይ አወለቁና በፓንት ብቻ ለውጌሻዋ አስረከቧት
…ውጌሻዋ ተመሳሳዩን እሽት ከጭኖቾ ጀመረው ወደታች መውረድ ጀመሩ…ቀኝ እግሯ ቁርጭምጭሚቷ ጋር ደርሰው ጨበጥ..ጨበጥ ሲያደርጓት ግን ከተኛችበት እንደመብረቅ አጓርታ ተነስታ ቁጭ አለች…ሁሉም በድንጋጤ የሚያደርጉት ጠፋቸው..‹‹አዎ እዚህ ጋር ችግር አለ‹‹አሁን በደንብ አድርጋችሁ ግራና ቀኝ ትከሻዋን ያዟት፡፡››የውጌሻዋን ትዕዛዝ ስትሰማ አይኖቾ በፍራቻ ተጉረጠረጠ፡፡በእድሜዋ መርፌ ለመወጋት እሩሱ በስንት እዝጊዎታና ማባበያ ነው...ታዲያ አሁን እንዲህ ላይቨ በስቃይ ስትፈተን እንባዋ ረገፈ
፡፡እናትና ልጅ ግራና ቀኛ ትከሻዋን አጥብቀው እንዳትነቃነቅ ያዙዋት..ሴትዬዋ እየጨመቁና እያሽከረከሩ ያሾት ጀመር…በህይወቷ ተስምቷት የማያውቀው አይነት ህመም…..ተሰማት..የሆነ መጋዝ ጥርስ ያለው አዞ በሁለት መንጋጋዎች መሀከል እግሮቾን አስገብቶ እያኘካት ነው የመሰላት..እንባዋ ብቻ ሳይሆን ንፍጦም በአፍንጫ ላይ እየተዝረከረከ እንደሆነ ይታወቃታል…ለዛ ግን የምትጨነቅበት ሁኔታ ላይ አይደለችም…..ውጌሻዋ ከ10 ደቂቃ በኃላ የተሰበረውን አጥንት ወደቦታው ከመለሱ በኃላ እንዳይነቃነቅ በቀርከሃ በደንብ አድርገው ከሰሩት በኃላ በፋሻ ጠቅልለው አጠናቀቁ…ከዛ እቃቸውን ሰብስባው ተነሱ…ለሊሴ የራሷን ቢጃማ አለበሰችትና መልሰው አስተኞት፡፡
‹‹እልፍነሽ››
‹‹አቤት እማማ››
‹‹ለሜቻ ድሬደዋ ሀብታም ወንድም አለው እንዴ?

ከመጽሐፍት መንደር💠

19 Dec, 17:48


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-አራት

በፀሎት ከጠፋች ከአንድ ሰዓት በኃላ ነበር አባትዬው ዜናውን የሰሙት፡፡በመጀመሪያ የቤቱ ሰው ሁሉ ያሰበው የተለመደው የልብ በሽተዋ ተነስቷባት ተዝለፍልፋ የሆነ ቦታ ወድቃ ይሆናል ተብሎ ነበር ፡፡ለአንድ ሰዓት ያህል ጋርዶቹ ፤ ዘበኞቹና አስተናጋጆቹ ሳይቀር የቤቱ ጥጋጥግ ከ50 በላይ ክፍሎች አንድ በአንድ እየከፈቱ አንድም ቦታ ሳይቀር ፈልገው ጅባት ካሉ በኃላ ነበር የጋርዶቹ ሀላቃ ፈራ ተባ እያለ የአቶ ኃይለመለኮትን መኝታ ቤት ያንኳኳው….በለሊት ልብሳቸው ሆነው የልጃቸውን የልደት በዓል ምክንያት በድካም የዛለ ሰውነታቸውን አልጋ ላይ አሳርፈው ገና እንቅልፍ እንዳሸለባቸው ነበር በራፋቸው የተንኳኳው…በመጀመሪያ በህልማቸው መስሏቸው ነበር፡፡ በኃላ ግን የምርም ክፍላቸው እየተንኳኳ መኆኑን ገባቸውና እየተነጫነጩ አልጋቸውን ለቀው በንዴት ውስጥ ሆነው በራፉ ሊከፍቱ እየሄዱ ባሉበት ቅፅበት ከመኝታ ቤታቸው ቀጥሎ ካለው ከፍል ውስጥ ያሉት ወ.ሮ ስንዱ ድምፅ ሰምተውና ደንግጠው ክፍላቸውን ከፍተው እየወጡ ነበር፡፡ ሁለቱም በአንድ ጊዜ እያንኳኳ ያለው ጋርድ ላይ አፈጠጡበት፡፡
‹‹ምን ተፈጥሮ ነው?››

‹‹ጋሼ..እንዴት እንደሆነ አናውቅም…..ልጆቹ እየተከታተሏት ነበር….››ለማስረዳት አስቦ መንተባተብ ጀመረ..፡፡
‹‹ምን እያወራህ ነው?››
‹‹በፀሎት..››
‹‹በፀሎት ..ልጄ ምን ሆነች..?አመማት እንዴ…?የልብ ህመሟ ተቀሰቀሰባት?››እናትዬው በመርበትበት በጥያቄ አጣደፉት፡፡
‹‹አይ አላመማትም…ላለፉት አንድ ሰዓት ውስጥ ስንፈልጋት ነበር…የለችም…››
‹‹የለችም ማለት…….?››
‹‹ጓደኞቾ ደብቀው ይዘዋት ሄደው መሰለኝ…. ግቢው ውስጥ የለችም፡፡››
‹‹እንዴ ..ይሄ ምን ማለት ነው..?ያን ሁሉ ጠብደል ጎረምሳ በጠባቂነት የቀጠርኩት እንዲህ አይነት ነገር እንዲከሰት ነው እንዴ…?ሰውዬ የእያንዳንዳችሁን ግንባር በሽጉጥ ሳልነድልላችሁ ልጄን ካለችበት ፈልጉና አስረክቡኝ…፡፡››በመራር ንግግር ቀድሞም የደነገጠውን ሰውዬ ይበልጥ ፍርሀት ለቀቁበት፡፡
‹‹እሺ ጌታዬ… ሁሉም ሰው እየፈለጋት ነው፣ይሄንን ነገር እርሶም በሰዓቱ መስማት አለቦት ብዬ ነው ቀድሜ ያሳወቅኳት…››
‹‹ወይኔ ልጄን..ይሄ የእነሱ ሳይሆን ያንተ ጥፋት ነው…››እናትዬው ቁጣቸውን ወደባላቸው አዞሩት፡፡
‹‹ይሄ ደግሞ ምን ማለት ነው?››ባልና ሚስቶች የተለመደውን ጭቅጭቃቸውን ቀጠሉ፡፡
‹‹ልጄን እንደከብት እረኛ ቀጥረህባት ስታጨናንቃት ነው ለዚህ ያበቃችው፡፡››
‹‹ሴትዬ እስኪ አሁን ተይኝ….እኔ ለራሴ ግራ ገብቶኛል ይበልጥ ግራ አታጋቢኝ.››አሉን ፊት ለፊት እየሄደ ያለውን ጋርድ ተከትለው ኮሪደሩን አቆርጠው መሄድ ጀመሩ..፡፡ወ.ሮ ስንዱም ማጉረምረማቸውን በለቅሶ አጅበው የለበሱትን ቢጃማ እንኳን ሳይቀይሩ ከኃላ መከተል ጀመሩ…፡፡በፀሎት ግን ለሊቱን ሙሉ ብትፈለግ ..በየወዳጅ ዘመድ ቤት ቢደወል…በከተማ አውራ ጎዳናዎች ከሰላሳ በላይ መኪኖችን ተሰማርቶ ብትፈለግ ድካዋን ለማግኘት አልተቻለም…
በስተመጨረሻ የግቢው ካሜራ ቅጂ ለሁለተኛ ጊዜ በዝግታ ሲታይ ነው እራሷን በአለባበሶ ቀይራ ብቻዋን በሞተር ሳይክል ግቢውን ለቃ እንደወጣች የታወቀው፡፡ይሄ ደግሞ በቤተሰቡ ላይ የነበረውን ድንጋጤና ፍራቻ ይበልጥ አናረው..ምክንቱም አወጣጧ አስባባት መሆኑን ስለተረዱ….፡፡ከዛ አባትዬው አቶ ኃይለመለኮት ያላቸውን ተሰሚነትና ከመንግስት ሰዎች ጋር ያላቸውን ትስስር በመጠቀም ለእያንዳንዱ ፖሊስና ትራፊክ ፖሊስ ፎቶዋና የሞተር አይነትና ታርጋ ቁጥሩ ተበትኖ እንድትፈለግ መመሪያ እንዲተላለፍ ተደረገ ፡፡
በማግስቱም ምንም ፍንጭ ሳይገኝ በመንጋቱ እቤቱ ሁሉ በወዳጅ ዘመድ ተጨናነቀ፡፡..ወላጆቹ በስጋትና ፍራቻ ብቻ ሳይሆን በሰው ትንፋሽም መፈናፈኛ አጣ…አቶ ኃይለመለኮት ሲጨንቃቸው ከአጀቡ ተነጥለው ቀጥታ ወደልጃቸው መኝታ ቤት ገብና ከውስጥ ዘግታው አልጋዋ ጠርዝ ላይ ቁጭ ብለው ግድግዳው ላይ የተለጠፈውን ግዙፍ የልጃቸውን ፎቶ እየተመለከቱ በትካዜ መንሳፈፍ ጀመሩ....እንባቸው መቆጣጠር አልተቻላቸውም…እንደህፃን ልጅ ነው ተንሰቅስቀው ያለቀሱት….በህይወታቸው እንዲህ አይነት ለቅሶ መቼ እንዳለቀሱ ፍጽም ትዝ አይላቸውም….አዎ ልጃቸው የልብ ንቅለተከላ በተደረገላት ጊዜ በህይወታቸው በጣም ያዘኑበትና የተጨናነቁበት ጊዜ ነበር…በቀሪ ህይወታቸውም መቼም ተመሳሳይ ሀዘን ውስጥ እገባለሁ የሚል ግምት አልነበራቸውም….ግን ተሳስተው ነበረ..አሁን ያሉበት ጭንቀትና ስጋት ከዛን ጊዜም ከፍ ያለ ነው…. ፡፡ልጃቸው አንድ ነገር ብትሆን ምን እንደሚሆኑ ምንም የሚያውቁት ነገር የለም..፡፡ግን በእርግጠኝነት ሌላ ኃይለመለኮት እንደሚሆኑ ሳይታለም የተፈታ ነው..ምን አልባት አብደው ጨርቃቸውን ሊጥሉ ይችሉ ይሆናል...ወይንም ንዴታምና አውሬ አይነት ሰው ሊሆኑ ይችላሉ ….ልባቸው ፍስስ እያለባቸው ነው….አይናቸውን ከወዲህ ወዲያ እያሽከረከሩ የልጃቸውን እቃዎች በስስት ሲቃኙ አይናቸው አንድ ፖስታ ላይ አረፈ..በድንጋጤ ተነሱና ወደእዛው ተራመድ፡፡ አነሱት… ሁለት ነው…፡፡ከላዩ ላይ የተፀፈውን አነበቡት..፣አንደኛው ለአባዬ ይላል…ሁለተኛውን አዩት ለእማዬ ይላል…እሱን ጠረጴዛው ላይ መልሰው አስቀመጡና ለእሷቸው የተጻፈውን ይዘው ወደአልጋ ጠርዝ ተመላሱና ፖስታውን ቀደው ወረቀቱን በማውጣት ማንበብ ጀመሩ፡፡
አባዬ….እንዴት እንደምወድህ ታውቃለህ አይደል? በጣም ነው የምወድህ..ግን ሁሌ ትናፍቀኛለህ…፡፡ሁሌ እሩቅ ውጭ ሀገር ያለህ ነው የሚመስለኝ….እቤት እያለህ እራሱ የሌለህ መስሎ ነው የሚሰማኝ…እርግጥ አንተ ሁሉ ነገር ተሟልቶልኝ በቅምጥል የምኖር ደስተኛ

ልጅ ነው የምመስልህ…እየቀያየርኩ ምነዳችወ ከሶስት በላይ ዘማናዊ መኪናዎች አሉኝ፣በወር ከመቶ ሺ ብር በላይ በእጄ ይሰጠኛል….በየሄድኩበት እየሄዱ የሚጠብቁኝ ቁጥራቸውን የማላውቃቸው ጋርዶች አሉኝ……በአመት ሁለትና ሶስት ጊዜ የፈለኩትን ውጭ ሀገር ሄጂ እዝናናለሁ…በአጠቃላይ ኑሮዬ ለአብዛኛው ኢትዬጵያዊ በተረት አለም እንኳን ሰምቶት የማያውቀው የህልም አለም አይነት ነው…ግን እኔ በእድሜዬ እናትና አባቴ ሲሳሳሙ አይቼ የማላውቅ ልጅ እንደሆኑክ ማንም አያውቅም..አረ መሳሳሙ ይቅር አንድ መኝታ ቤት ውስጥ አብረው ሲያድሩ አይቼ አላውቅም… አይገርምም…..፡፡
አባዬ ልጅ ሆኜ እርግቤ እያልክ ነበር የምትጠራኝ..እርግቤ ስትልኝ እንዴት እንደምደሰት አታውቅም ፡፡የእውነትም ያንተ ነጭ እርግብ ሆኜ አድማሱን ሰንጥቄ በሰማይ መብረር የምችልና ጨረቃ ጋር ደርሼ ከዋክብቶችን ጨብጬ ምጫወትባቸው ይመስለኝ ነበር…ባቃ ትንሽ መልአክ እንደሆንኩ እንዲሰማኝ ነበር የምታደርገው..ግን አባዬ አንተ ያልተረዳኸውነ ነገር እኔ ከ19 ዓመቴ በኃላ ማለቴ የሌላ ሴት ከሰውነቴ ካወሀድኩ ጀምሮ እኔ እኔን አይደለሁም…..ትዝ ይልሀል እርግቤ አትበለኝ በስሜ ጥራኝ ብዬ ያስተውኩህ እራሴው ነኝ..ለምን ብለህ ጠይቀኸኝ ግን አታውቅም..ምን አልባት ዝም ብዬ እርግቤ የሚለው ሰም ደስ ስለማይለኝ መስሎህ ሊሆን ይችላል እንደዛ ግን አይደለም….ከልብ ነቅለ-ተከላ ከተደረገልኝ በኃላ ክንፏ የተሰበረባት መብረር የማትችል እና በየጓሮ የምትንፏቀቅ እርግብ እንደሆንኩ እየተሰማኝ ስለመጣ ነው ያስቆምኩህ..ለአንድ ልጅ እኮ በሰማይ እንዳሻት እንድትበር የሚያደርጋት የአባቷ ፍቅር ቀኝ ክንፍ እና የእናቷ ፍቅር ግራ ክንፍ ሲሆናት ነው….የወላጆቾ ፍቅር ነው እንድትበር የሚያደርጋት….ያ እንደሌለኝ ስረዳ ነው ስሙ ያስጠላኝ፡፡ለምን እንደሆነ አላውቅም ከድሮዬ በተለየ ፍቅር

ከመጽሐፍት መንደር💠

19 Dec, 16:34


ጉዞ በፀሎት የተሰኘዉ ልቦለድ ይለቀቃል adminu አልተመቼዉ ሆኖ ነዉ ☺️

ከመጽሐፍት መንደር💠

16 Dec, 17:02


ጉዞ በፀሎት(አቃቂ እና ቦሌ)
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
ምዕራፍ-ሶስት

በፀሎት የልብ ንቅለ ተከላ ካደረገች በኃላ ልክ እንደዛሬው አይነት በህይወቷ ወሳኝ የሆኑ ትላልቅ ውሳኔዎችን አሳልፋለች….አንዳንዴ‹‹ በእውነት እንዲህ እያሰብኩና እያደረኩ ያለሁት እኔው ነኝ?››ብላ በራሷ እስክትደመም ድረስ ነበር ለውጦ፡፡

‹‹አሁን የሌላ ሰው ለዛውም የሞች ንፅህ ልብን በሰውነቴ ተሸክሜ ርካሽ የሆነ ስራ ፈፅሞ አልሰራም››የሚል አቋም ላይ ደርሳ በዛ መሰረት ነው የምትንቀሳቀሰው…ትንሽ ለስሜቷ የማይመችና የሚቆረቁር ነገር ሲያጋጥማት እንደድሮው ‹‹ቆይ እስኪ ልሞክረው›› ብላ ዘላ አትገባበትም….ጊዜ ወስዳና ተረጋግታ ታስብበታለች..ነገሩን ትመዝንና እሷንም ሆነ ሌላውን ሰው የሚያሳዝንና የሚያስከፋ መስሎ ከተሰማት ወዲያው መንገዷን ታስተካክላለች….ይሄ በብዙ ነገሮች ጠቅሟታል…ግን ደግሞ ቤተሰቦቾን በተመለከተ እንደበፊቱ ነገሮችን አይታ እንዳላየች እንድታልፍ አላደረጋትም…እያንዳንዱ በመሀከላቸው ያለው ጥላቻና ጥል በጣም ያስጨንቃትና እረፍት ይነሳት ጀመር…ለምን ብላ እንድትጠይቅ..ጥፋቱ የማንኛቸው ይሆን እያለች እንድትመረምርና ፣እንዴት ሊስማሙና ትክክለኛ ባልና ሚስት ሆነው ለእሷም መቼ እንደ ትክክለኛ ወላጅ የምትፈልገውን ፍቅር ሊለግሶት እንደሚችሉ ማለምና መተከዝ የጀመረችው ከበርካታ ወራቶች በፊት ነው፡፡
በፀሎት  ጨረቃ በነገሰችበትና ከዋክብቷች ሰማዩ ላይ ተበትነው በሚንሸራሸሩበት በዛ ውድቅት ለሊት እቤቷን ጥላ ..ከእናትና አባቷ ርቃ …ከጋደርዶቾ አምልጣ መሄዷን እንጂ ወዴት እንደምትሄድ ለምን ያህል ሰዓት መንዳት እንዳለባትና የመንገዷ ማዳረሻ የት እንደሆነ ምንም የምታውቀው ነገር የለም፡፡ዝም ብላ ብቻ በዛ ውድቅት ለሊት የአስፓልቱን መሀከል ይዛ በመድሀንያለም ቤተክርስቲያንን አጠር ተኮ በሚገኘው መንገድ ወደፊት በመውጣት ዋናውን አስፓልት ገባችና ቀጥታ ወደ ስቴዲዬም ሚወስደውን መንገድ ያዘች….መስቀል አደባባዩን እንደጨረሰች ወደግራ ታጠፈችና ወደላንቻ የሚወስደውን የአስፓልት መንገድ ያዘች..
ከትራፊክ መጨናነቅ ነፃ የሆነውን መንገድ በፍጥነት መጋለብን ተያያዘችው…ምንም ሳታውቀው ለአንድ ሰዓት ያህል ከነዳች በኃላ አቃቂ ድልድይ ጋር ስትደርስ ወደቀኝ ተጠማዘዘችና ወደአቃቂ የሚወስደውን መንገድ ገባች ፣…መንዳቷን ቀጠለች…ድንገት ተረጋጋችና ሞተሩን አቀዝቅዛ አቆመችና አካባቢውን ስታስተውል የምታውቀው ሰፈር ሆኖ በማግኘቷ ደነገጠችም.. ተገረመችም….እዚህ ሰፈርና እዚህ ቦታ ለመምጣት ባለፈው ሁለት አመት ስትመኝ ነበር….ቢያንስ በሳምንት አንድ ቀን በህልሟ እዚህ አካባቢ መጥታ ስትዳክር ነው የምታየው..ግን መጥታ የምትፈልገውን ነገር ለማድረግ አባቷ ሊፈቅድላት አልቻለም..ለጠባቂዎችም በጥብቅ ስለተነገራቸው እንኳን አሁን ያለችበት ሰፈር ይቅርና ክፍለከተማው ውስጥም ዝር እንድትል እንዳይፈቅዱላትም ፤ከዚህ ቀደም ምንአልባትም ከአመት በፊት ሰፈሩንና እቤቱን ለአንድ ጊዜ በስንት ጭቅጭቅ ያሳያት እራሱ አባቷ ነበር፡፡

በጊዜው መኪናዋን አሁን ሞተሯን ያቆመችበትን ቦታ አቁሞ…የቤቱን በራፍ በጥቁሩ የመኪና መስታወት ወደውጭ እየጠቆመ…‹‹አየሽ የልጅቷ ቤተሰቦች የሚኖሩት እዚህ ነው..እኛ አሁን የሚገቡት አባቷ ናቸው…አብሯቸው ያለው ደግሞ ልጃቸው ነው….እናትና እህቷም አሉ››እያለ ነበር ያብራራላት፡፡
‹‹አባዬ እንዲት እንዲህ ጭንቁርቁስ ያለ ቤት እንዲኖሩ ትፈቅዳለህ..?እየው እስኪ አጥሩን..እቤታቸውን ተመልከተው››በምሬት አባቷን መጠየቋን ታስታውሳለች፡፡
‹‹ልጄ ምን ላድርግ ?በግድ በወታደር አስገድጄ ሌላ ቤት ውስጥ እንዲገቡ ማድረግ አልችል››
‹‹ማለት…?››
‹‹ነግሬሻለሁ እኮ …ቤተሰቡ ከእኛ አምስት ሳንቲምእንደማይቀበሉ ምለው ነው የነገሩን››
‹‹አባዬ ይሄ ምንም ሊገባኝ አልቻለም…የተሸከምኩት እኮ የልጃቸውን ልብ ነው….በልጃቸው ሞት እኮ ነው አሁን እኔ በህይወት መኖር የቻልኩት…አልገባህም አባዬ …ለምን እሷ ሞታ እኔ ኖርኩ..?እግዚያብሄር ይሄን እንዴት ፈቀደ…?.አባዬ በየቀኑ የጥፋተኝነት ስሜት እየተሰማኝ ነው…እየተሰቃየሁልህ ነው…››
‹‹አውቃለው  ልጄ…እነሱ  ፍቃደኛ  ቢሆኑ  እኔ  የሀብቴን  ግማሽ  እንኳን  ብሰጣቸውና
..ላደረጉልኝ ነገር ምስጋና ባቀርብ ደስ ይለኝ ነበር…ግን ተቀባይ ከሌላ መስጠት ስለፈለግሽ ብቻ አይሳካልሽም፡፡››
‹‹ቢሆንም አባ ..እኔ ልቧን ሰጥታኝ ህይወቴን እንዲራዘም ያደረገቺኝን ልጅ ቤተሰቦች እንዲህ በጉስቁልና እንዲኖሩ አልፈልግም…..ልጃቸው በህይወት ኖራ ቢሆን ትጦራቸው ነበር…የሆነ የሆነ ነገር ታደርግላቸው ነበር….ብቻ አላውቅም የሆነ ዘዴ ፍጠርና እርዳቸው፡፡››
‹‹አይ ልጄ አልገባሽም እንዴ…ልጃቸው ላንቺ ልብ ከመስጠቷ ከአመታት በፊት በእኛ ፋብሪካ የሚሰራውን ወንድ ልጃቸውን እራሱ ስራ እንዲለቅ አድርገውታል…..ለማንኛውም የተቻለኝን እሞክራለው..አሁን ይሄን ያህል ካየሻቸው ይበቃሻል… አንሂዱ ››ብሎ ነበር ከአካባቢው ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የለቀቁት፡፡

ከዛ ወዲህ ግን ፍፅም ወደአካባቢው እንድትጠጋና ከቤተሰቡ ጋርም በምንም አይነት መንገድ ተገኛኝታ እንዳትተዋወቅ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ተሳክቶላቸዋል…አሁን ግን ይሄው በደመ ነፍሷ ከቤቱ ፊት ለፊት አስፓልቱ ጠርዝ ላይ ሞተሯን አቁማ ቁልቁል አዘቅዝቃ እያየችው ነው፡፡
‹‹ወደእዚህ መምጣት በአእምሮዬ ስሌት ውስጥ አልነበረም….ሳስበው ግን የልጃችሁ ልብ ነው እየመራ እዚህ ድረስ ያመጣኝ››ስትል አጉረመረመች፡፡ድንገት ስሜታዊ ሆነችና ነዳጁን ረገጠችና ጨምቃ የያዘዘችውን ፍሬን ለቀቀች…አስፓልቱ ን ለቃ ቀጥታ ወደቤቱ አቅጣጫ መንዳት ጀመረች …የሞተሩ ፍሬን ድንገት እምቢ አላት… ያ ደግሞ ጠቅላላ ሰውነቷ በፍራቻ እንዲቀዘቅዝ ነው ያደረጋት…ሞተሩ ከቁጥጥሯ ውጭ እየወጣ ነው.. መንገድን ሰታ ወደቀኝ እየተጓዘች ነው…›የተውሸለሸለ የእንጨት አጥር ቤት ጥሳ ገባች…. የቆርቆሮ በር ካለው ሰርቢስ ቤት በራፍ ጋር ተላትማ በአየር ላይ ተንሳፈፈችና መሬት ላይ ጧ…ጧጧ ብላ ወደቀች....ሞተሩ አጥሩን ጥሶ ሲገባና ከቆርቆሮ በራፉ ሲጋጭ የፈጠረው ድምፅ የፍንዳታ አይነት ነው….እሷ ወዲያው ነው ጭልም እያለባት የሄደው…እንዲህ ባለ ሁኔታ እራሷን አደጋ ላይ የመጣል እቅድ አልነበራትም…….ከቤት ውስጥ ግን ቡዙ ጫጫታና ትርምስ ተሰማ…
‹‹አማዬ ምንድነው……?››
‹‹.ልጆቼን ..››
‹‹ልጆቼን ››
‹‹አባዬ ሰላም ነህ?››
የሶስት ወይም የአምስት ሰዎች ድምጽ እየተሰማት ነው….እያንዳንዱ ድምፃ ልቧ ላይ እየተንጠባጠ እያቀለጣት ያለ ነው የመሰላት፡፡‹‹ምን ሆኜ ነው …?ምን ተፈጠረ…?ይሄን እያሰበች ሳለ ጭልም እያለባት ሄደ ፣እንደምንም ላለመጥፋት ብትሞክርም አልቻለችም
…እራሷን ሙሉ በሙሉ ሳተች….፡፡እቤቱ ውስጥ ያለ አንድ ጎረምሳ እና አንድ ወጣት ሴት… እናት አባት በዛ ውድቅት ለሊት ፈጣሪ ምን አይነት መብረቅ እንደላከባቸው ለማወቅ በሀይለኛ ድንጋጤ እንደተመቱ የተተራማመሱ የቤታቸውን በራፍ እንደምንም ተራ በተራ እየተጋፉ ወደውጭ ወጡ….የውጭ መብራት አብርተው ሲመለከቱ ..ከበራፉ በሶስት ሜትር ርቀት መሬት ላይ የተዘረጋ ጥቁር እና ነጭ ቀለም የተቀባ ዘመናዊ ሞተር ሳይክል ይታያል...ከሳይክሉ ሁለት ሜትር ርቀት አንድ ሄሌሜት ያደረገ ባለመካከለኛ ቁመት ሰው እጥፍጥፍ ብሎ ወድቆ ይታያል....ሁሉም በቃል ሰይነጋገሩ እየሮጡ ሰውዬውን ከበቡት…

ከመጽሐፍት መንደር💠

15 Dec, 16:34


እልልታ
ጭብጨባ
ከአውደ ምህረቱ ተነስቶ ይነፍሳል፤
የሰማእቷ ታ'ምር እንደ ጉድ ይወሳል።

"ሰምታኛለች እናቴ..."
"ታውቃለች አርሴማ..."
ክብሯን የሚመጥን
ይገባል ስለት - ጧፍ፣ ጥላ፣ ብር፣ ሻማ።

ሰው ይጸልያል
ሰው ይለምናል ክፍተቱን አይቶ፣
እኔ ከንቱ ግን
የጎደለኝን አላውቅም ከቶ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፣
ደጅሽን ስረግጥ እታደሳለሁ።

እዪኣት ያቺን ሴት
ከአትሮንሱ ጀርባ የምትዘምረው
ስምሽን ደጋግማ የምታነሳው፤
እኔ እስከማውቃት
ፊደል የሚያንቃት
ኩልትፍ አንደበት - ነው የነበራት።

ምን ጸልያ ነው አፏ የተፈታ?
ምን ብላሽ ይሆን
ቃል አቅሙን አጥቶ ለእሷ የተረታ?
የእኔማ ምላስ አግድም ለፋፊ
ለ'ንቶ ፈንቶ እንጂ ለጸሎት ታጣፊ።

እይው ያንን ሰው
ኑሮ የደቆሰው
የደስታን እንባ ሞልቶ ሚያፈሰው፤
እኔ እስከማውቀው
ሞት 'ሚናፍቀው
ማጣት በዝቶበት ገዳይ ሚፈልግ
ተስፋን ተነጥቆ
አለመኖርን የሚያነበንብ።
ምን ሰጥተሽው ነው ፊቱ የፈካ?
ምን አግኝቶ ነው
የደስታው መጠን ጣሪያ የነካ?
እኔ ሳቅ አላውቅ እንባም አይገደኝ
መኖርም መሞት ትርጉም አይሰጠኝ፤
ብቻ እመጣለሁ
ብቻ አይሻለሁ፤
ደጅሽን ስረግጥ ነፍስ እገዛለሁ።

#ኤልዳን

ከመጽሐፍት መንደር💠

13 Dec, 19:37


#የኢትዮጲያው
ሰይጣን
#ለአውሮፓው
ሰይጣን የጻፈው
ደብዳቤ» በአዜብ መሰለ
****
እንደምነህ ሰይጣን ያውሮፓው ወንድሜ
እኔ አለሁ በመዝሙር በፀሎት ደክሜ።
😴
“አይጥ ሞቷን ስትል ስታበዛ ሩጫ
ሄዳ ታሸታለች የድመት አፍንጫ።”
የሚሉት ሆኖብኝ ኢትዮጲያ መጥቼ
ይኸው እነሳለሁ ዕለት ዕለት ሞቼ።
አንተ ግን እንዴት ነህ?
እነዴት ነው አውሮፓ ነዋሪው በሙሉ?
‘ቸርች’ ሰርተውልህ
ስምህን በመጥራት
#ያመልኩሀል
አሉ።
😋
የእኔን አትጠይቀኝ…!
😔
እዚህ
#በመስጊዱ
በአራቱም ማእዘን በዱዓ በፀሎት
አላህ ነው ሚወደስ…
🙄
እሱ ነው ሚመለክ ሰርክ ቀንና ሌት።
እኔማ መሮኛል…!
ዘወትር መዋረድ ነጋ ጠባ ቅሌት።
ግን አንተ እንደም’ነህ?
🫡
ታገኛቸዋለህ ናኒን እና ሩኒን
‘ህይወት’ ሰጠሀቸው በመርፌ በኪኒን?
እዚህ
#ኪኒን
ብትሰጥ የለም የሚቀበል
ሁሉ
#ዳንኩኝ
ይላል እየጠጣ
#ፀበል
😏
እኔማ ተቃጠልኩ…
🤬
እዚም እዛም ስፍራ ውሃ እያፈለቁ…
“በስመአብ ወወልድ” በስመ ስላሴ እያሉ ሰው እያጠመቁ
ስንቱን
#የያዝኩትን
በግድ
#አስለቀቁ

😠
አንተ ግን እንዴት ነህ?
🤔
እንዴት ነው አውሮፓ ጎዳናው መንገዱ?
ለማኞቹስ አሉ?
“ሆምለስ” ብለው ፅፈው ብሶት የሚያስረዱ።
እዚ ያሉ ለማኞች አቤት ሲያናድዱ!
“ምስኪን”ብለው ፅፈው ማሳጠር ሲችሉ
በአዛኚቷ
#ማርያም
በእግዚአብሔር እያሉ…
🙏
የሰው አንጀት በልተው፤
የእኔን አንጀት ደሞ ያንጨረጭራሉ።
🥶
ደሞ ሙስሊሞቹ አያተል ኩርሲን
አጣቅሰው ሲቀሩ
#ብረር
ብረር ይለኛል ከሰፈር ካገሩ።
አንተ ግን ደህና ነህ?
እዛ አገር እንዴት ነው?
ወጣቱ ፈጣን ነው? ወይስ ይዘገያል?
በጭፈራ መሀል…
💃
🕺
ያንተን
#ቀንድ
፣ያንተን ዐይን
#ምልክት
ያሳያል?
☹️
እዚህ ‘እኔን ተወኝ…!
😴
የሀበሻ ነገር ባህሪው ይለያል።
ጭፈራ ቤት ገብቶ _
መጠጥ ሊጠጣ ያዝ‘ና
#በደሌ
‘ሚያስከፍተው ዘፈን…
“እመቤቴ ማርያም አርጊልኝ
#የግሌ
”።
/ ኧ…ረ …! እንደው እ…ድ…ሌ! /
🤦‍♂
እኔ አንድ ሀሳብ አለኝ…
··
ላንተ ይቀርብሀል
#ዩኔስኮን
ካገኘህ ‘ ባክህ ንገርልኝ
ይቺን ጉደኛ ሀገር
🇪🇹
“ለሰይጣን ‘
#ማትመች
” ብሎ ይመዝግብልኝ😂😂

ካነበብኩት🤗🤗🤗

ከመጽሐፍት መንደር💠

13 Dec, 19:33


የአብ!

በአምሳሉ በጥበቡ
          የሰራን፣
ኩሎ በምግባር
        የፈጠረን፣
በህጉ ስር የምንኖር፣
በሰው አምሳል ተገኝቶ
          የሚመክር፣
እኛ ነን ልጆቹ እኛ ነን
           ተማሪዎቹ፣
ደሙን በቀራኒዮ
     እርቃኑን ተሰቅሎ ያበቃን
                ደቀመዝሙሮቹ፣
የአብ ስራ የወልድ
       የመንፈስ ቅዱስ፣
ባሪያዎች የምናመሰግን
        የሚያኖረን በመቅደስ፣
ለዕምነታችን ተገዝተን፣
በነጭ ልብስ በመላዕክት
               ታጅበን፣
የድል ዜማ በዳዊት ዝማሬ
              እያመሰገንን፣
ምድራዊውን አለም እረስተን፣
ከሰማይ ከዋክብት በላይ
               አብርተን፣
ከፀሀይ ሰባት እጅ በላይ
     ብርሀን ከሆነው ቤት ተገኝተን፣
በዕልልታ በሽብሸባ
        ምስጋናን እያቀረብን፣
ልባችን ሳይስት ለቃሉ
            ታማኝ ሆነን፣
ያብቃን ለዛን ጊዜ ለምህረት
          ለሰዓቱ፣
ያኑረን ከዕቅፉ በገነት
          በክብራዊ መንግስቱ።☺️

ከመጽሐፍት መንደር💠

13 Dec, 17:09


..............


ከማበዴ በፊት፤ኣንድ ቃል ልንገርሽ
ላንቺ ብዬ ኣይደለም፤ጨርቅ የምቀድልሽ
ስለተውሺኝ ብዬ
መራቅ መገፋቴን፤መቻል ስላቃተኝ
ፍቅርሽ እንደ ቅዘት፤ስለሚያቃትተኝ
ከምቀደው ልብሴ፤ከገላዬ ካለው
ትዝታሽ ብቻ ነው፤በውብ የተሳለው
ጠረንሽ ነው ያለ፤ከገላ ከጨርቄ
የሄድሽ ቀን ጣልኩት፤ሀፍረቴን ኣውልቄ
    ከማበዴ በፊት
ኣንድ ቃል ለናገር፤ፍቅርዬ ባንቺ ፊት
  ኡ ኡ ብዬ ብጮህ
እንዳትጠብቂ ከጬኀቴ መሀል
ከቶም ስምሽ የለም
የኔ ውድ የኔ ኣለም
ለኔ ኣይነቱ ኣፍቃሪ
እብደት ጤንነት ነው ከእስሩ መፈቻ
ኣንቺን አንቺን ብቻ
ማለቱን እረስቶ
ፍቅርን እንደጨርቅ፤ከገላው ለይቶ
     ከገረባው መሀል
ተግቶ ሊፈልጋት፤የጠፋችው ፍቅሩን
ቅጠሏ ኣመርቅኖ
ግንዷ የበከለ ሰማይና ምድሩን
    ቅጠሏ ፍቅር ነው፤ሙትን የሚባብል
ግንዷ ደሞ ግፍሽ፤በቁም የሚገድል
  ለዚህ ይሆን ? እብድ ሁሉ
ገረባ የሚያነሳ፤ገረባ የሚጥለው
የጠፋችው ፍቅሩን፤ስለምትመስለው
       እናም ፍቅርዬ
    ላብድ ስለሆነ እንዳትጸጸቺ
ኣንቺን ፍለጋ ነው፤የማበዴ ፍቺ
ከሰው መሀል ባጣሽ፤ካትሮንስ ባትገኚ
ኣብጄ ፈለኩሽ፤ገረባ ስትሆኚ


      

ከመጽሐፍት መንደር💠

07 Dec, 11:54


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-32
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ሶስት ኢትዬጵያዊ ታጋቾች በአማዛን ጥልቅ ማህፀን ውስጥ በጋንግስተሮች ዙሪያቸውን ተከበው
ውጥረት ያለበት ህይወት መግፋ ከጀመሩ አንድ ሳምንት  አለፋቸው፡፡በእያንደንዱ ቀን የሆነ ተአምር ይፈጠርና ነፃ እንሆናልን የሚል ጉጉት ውስጣቸውን ሲንጠው ነው የከረመው…በጣም አስጨናቂው ነገር ደግሞ  ኑሀሚ ቦታው ላይ ደርሳ ልደታቸውን ካከበሩበት ቀን በኃላ ዳግላስ አላዩትም…..የሚያስፈልጋቸውን ነገር የሚያደርጉላቸው  ወደውጭ አስወጥተው ግቢውስጥ እንዲናፈሱ የሚያደርጎቸው እሱ የመደባቸው ሰራተኞች ናቸው፡፡ይሄ ጉዳይ ደግሞ ይበልጥ አሳስቧቸዋል….

አሁን ግቢ ውስጥ ባለ ለመናፈሻ እንዲያገለግል በተሰራና ዙሪያውን በአበባ ባጌጠ አረንጓዴ መናፋሻ ቦታ ተጠጋግተው ተቀምጠዋል…ከእነሱ በአስር ሜትር ርቀት አምስት የሚሆኑ ጠባቂዎች ሙሉ ትጥቃቸውን እንደታጠቁ ፈንጠርጠር ብለው እየጠበቋቸው ነው፡፡እንደተለመደው ግቢውን የሚጠቡቁ ደግሞ ቁጥቸው በውል የማይታወቁ በየሰዓቱ ፈረቃቸው የሚቀያር መደበኛ ጠባቂዎች በየአስር ሜትሩ በተተከለ ማማ ላይ ከባባድ መሳሪያቸውን ወደውጭ ደቅነው …አካባቢውን በንቃት እየተጠባበቁ ነው፡፡በእውነት ይሄንን ሁኔታ የሚያይ ማንኛውም ግለሰብ ይሄ በእንዲህ አይነት ጥንቃቄ የሚጠበቀው ግቢ የግለሰብ መኖሪያ ሳይሆን የሀገር መሪ ቤተመንግስት ነው የሚመስለው፡፡

‹‹የእኔ ማር ሰውዬሽ መች ነው ተመልሶ የሚመጣው?››ምስራቅ ነች ኑሀሚን የጠየቀቻት፡፡
‹‹ምነው እኔ ሳይናፍቀኝ አንቺን ናፈቀሽ እንዴ?››ስትል አሽሙሯን በአሽሙር መለሰችላት፡፡
‹‹የእውነት  አሁን ያለንበት ሁኔታ ግራ የሚያጋባ ነገር ነው….ነገሮች ለቀናት ምንም ለውጥ ሳያሳዩ ባሉበት ዝም ሲሉ ያስፈራል፡፡በተለይ እንዲህ እኛ ባለንበት ሁኔታ ላይ ለሆነ ሰው ነገሮች እንቅስቃሴ አልባ ሲሆኑ ያሰለቻሉ…››አለች ምስራቅ፡፡

‹‹እኔ ግን ብዙም አልሰለቸኝም….በአለም ላይ በጣም ከምወዳቸው ሁለት ሰዎች አጠገብ ነው ያለሁት….››ሲል ተናገረ ናኦል፡፡የተናገረው የእውነት የሚሰማውን ነገር ነው፡፡እርግጥ አሁን ያለበት ሁኔታ ለህይወታቸው ዋስትና የሌለው በማንኛውም ሰዓት ምንም አይነት ነገር ሊደርስባቸው የሚችል እንደሆነ ያውቃል…፡፡ግን ደግሞ ከዚህ ሁኔታ በሆነ ተአምር ነፃ የሆነ ወደሀገር መመለሳቸውንም በፈንጠዝያ ሚጠብቀው የምስራች አይደለም፡፡ምክንያቱም ከነፃነት በኃላ  ምስራቅን የማጣት ስጋት አለበት፡፡ተልኮቸን በድል ተጠናቋል ከአሁን ወዲህ ፍቅር ፍቅር የምንጫወተው ነገር ትርጉመ ቢስ ስለሆነ እዚህ ላይ ያብቃና ወደበፊት  ሁኔታችን እንመለስ ትለኛለች የሚል ከፍተኛ ስጋት አለው…..ለዛ ነው ነጻነቱን ልክ እንደምስራቅ እና እህቱ ኑሀሚ አብዝቶ የማይናፍቀው፡፡

‹‹ግን ሰዎቻችን ምልክቱ አልደረሳቸውም ማለት ነው….እንዴት እስከአሁን አንድ ነገር ሳያደርጉ››ኑሀሚ ነች ምስራቅን የጠየቀችው፡፡

‹‹እርግጠኛ ነኝ ምልክቱ  ያለንበት ቦታ በትክክል ይነግራቸዋል…ግን ደግሞ እንደምታይው አካባቢው የአማዞን ብብት ስር ነው የሚገኘው…ጉዳዩን አስመልክቶ የአካባበውን መንግስታትን ማሳመንና የእነሱን እርዳታ ማግኘትም ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ድርድር የሚጠይቅ ውስብስብ ጉዳይ ነው፡፡ምን አልባት ሰውዬው አሜሪካን ጨምሮ በአካባቢው መንግስታት ጥቁር መዝገብ ላይ የሰፈረ…በአለም አቀፍ አሸባሪነት መዝገብ ላይ ተመዝግቦ በየስርቻው የሚፈለግ በመሆኑ የኢንተርፖልንም ሆነ የኤፍ.ቢ.አይን ቀልብ ሊስብ እና ከአነሱ ተገቢው እርዳታ ለማግኘት የሚያስችል ይመስለኛል፡፡ያ ከሆነ ደግሞ በቅርቡ የሆነ ነገር እንጠብቃለን ማለት ነው…በዛ ላይ ያንቺም አፍቃሪ በገባው ቃል መሰረት የሆነ ነገር ሊያደርግ  ይችል ይሆናል፡፡

‹‹እሱ እንኳን ቢችል ኖሮ እስከአሁን የሆነ ነገር ያደርግ ነበር…እኔን ለማዳን በዚህ አስፈሪ ጫካ ውስጥ ብቻውን ሲባክን የሆነ አውሬ እራት ሆኖ ቢሆንስ የሚል ፍራቻ ውስጤን እየበላው ነው፡፡››አለች ቅዝዝ ብላ፡፡

ምስራቅ ኑሀሚ የምትናገረውን ቃል ብቻ ሳይሆን የስሜቷን መቀያየር ጭምር በትኩረት እየተከታተለች ነበርና ‹‹ውይ ትንሿ እህቴ ጉድ ሆነሻል››አለቻት፡፡
‹‹ማለት?››

‹‹ከልጁ ፍቅር ይዞሻል አይደል?››አለቻት፡፡

‹‹አይ አልያዘኝም…››ብለ የመከላከያ ሀሳቧን ታቀርባለች ብላ ጠብቃ ነበር…ኑሀሚ ግን ይበልጥ በሀሳብ ውስጥ ገብታ ጭልጥ ብላ ጠፋች፡፡በመካከላቸው ረጅም ፀጥታ ሰፈነ..ግን ድንገት አንደበቷ ተከፍቶ ማውራት ጀመረች‹‹ብታይው በጣም ደስ የሚል ልጅ ነው….ይሄንን የአማዞን ደን ልክ እንደፍቅረኛው ነው የሚወደው…ስለእያንዳንዱ እንስሳትም ሆነ የዛፍ አይነቶች ጥልቅ የሆነ እውቀት አለው…ከጭንቅላቱ የሚፈልቀው እውቀት ልክ እንደአማዞን ወንዝ ጥልቅና ሩቅ ነው፡፡ሰውን ሲንከባከብ እንደእናት ነው፡፡ከአደጋ ሲጠብቅሽ አባትሽን ነው የሚመስለው…ቀልድ ይችላል…..በቃ ምን ልበልሽ ሁሌ ከጎንሽ እንዲሆን ምትመርጪው አይነት ልዩ ሰው ነው፡፡እናንተ ወደእዚህ መጥታችሁ ዳግላስ እጅ ባትገቡና በጀመርነው መንገድ አምልጠን ቢሆን ኖሮ አብሮኝ ወደኢትዬጵያ ለመብረር ወሰኖ ነበር…ልንጋባ ነበር…››ስሜቷ ገንፍሎ እንባዋ መንጠባጠብ ስለጀመረ ንግሯን መቀጠል አልቻለችም፡፡

ናኦል ልክ እንደእሱ ሁሉ እህቱ ጥልቅ በሆነ የፍቅር ፍላፃ መመታቶ ስላዛዘነው ከተቀመጠበት ተነሳና ስሮ ቁጭ ብሎ አቅፎ ደረቱ ላይ አስተኛት‹አይዞሽ እህቴ…በሆነ ተአምር ነገሮች ይስተካከላሉ….በፍቅር መያዝ ምን ማላት እንደሆነ በደንብ ይገባኛል…ያፈቀርነውን ሰው እስከወዲያኛው የማጣት ስጋት ምን ያህል ነፍስን እንደሚያስጨንቅም አውቀዋለው…..አይዞሽ ነገሮች ሰላም ይሆናሉ…ደግሞም…››ንግሩን ሳይጨርስ የአንድ ወታደር ቅፅበታዊ ጨኸት የታከለበት ትዕዛዝ አስቆመው…

‹‹ተነሱ በቃ …ለመናፈስ የተፈቀደላችሁ ጊዜ ተገባዶል፡፡ወደክፍላቹ ተመለሱ››የሚል ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ሶስቱም ከተቀመጡበት ተነሱና ፊታቸውን ወደህንፃው አዙረው መራመድ ጀመሩ…ከኃላቸው ሲከተላቸው የነበረው ጠባቂ …..‹‹አንቺኛዋ ማነሽ››ሲል ወደኑሀሚ እየተመለከተ ጠየቀ፡፡

ዞረችና ‹‹አቤት..ምን አጠፋው?››ስትል አፈጠጠችበት፡፡

‹‹ቁሚ እስኪ››

ምን እየተፈጠረ እንደሆነ ሶስቱም ስላልገባቸው ሁሉም ባሉበት ቆሙ
ሰውዬው ሁለቱን ችላ አለና ቀጥታ ወደኑሀሚ ተጠግቶ የመሳሪያውን ማንገቻ በአንገቱ ከተተና በጀርባው አዙሮ አንጠለጠለው..ከዛ ሁለቱን እጆቹን ነፃ አድርጎ ተጠጋት…በተሰባረ እንግሊዘኛ ‹‹በኪስሽ ምንድነው የያዝሽው?››ሲል የተጨማደደ ፊቱን እንዳጨለመው ጠየቃት፡፡

ይበልጥ እየተጠጋችው‹‹ምን ያዝኩ ?ምንም….ከፈለክ ፈትሸኝ››አለችው፡፡

‹‹አይ ተይው በቃ›› ይለኛል ብላ ጠብቃ ነበር፡፡ እሱ ግን ከላይ ጀምሮ ነካ ነካ እያደረገ ፈተሸና ኪሷ ውስጥ እጆቹን ከቶ መፈተሸ ጀመር…ኑሀሚ ንዴቷ እንዳያሸንፋትና ይሄን እየተፈታተናት ያለውን ሰው መሳሪያውን ነጥቃ  በሰውነቱ ላይ በማርከፍከፍ ወንፊት አድርጋ ልትጨርሰው የሚፈታተናትን ስሜት እንደምንም አግታ አስቀረችው፡፡

ፈተታሸና‹‹…በቃ ቀጥሉ፣፣፣ደግሞ ፊኛሽ ተነፍቷል…ክፍል እንደገባሽ ወደ ሽንት ቤት ግቢና ሽንትሽን ሽኚ››የሚል ትእዛዝ አስተላለፈ….
ምንድነው የምታወራው…የምን ሽንት ቤት ነው››
እንግዲህ ነገርኩሽ…ወደሽንትቤት ግቢ››ብሎ ቀድሞ ወደህንፃው መራመድ ጀመረ..

ከመጽሐፍት መንደር💠

07 Dec, 11:54


ናምሮድ
ናምሮድ ፈጣሪውን አለ <ምድርን ለኔ ስጣት>. ፈጣሪም አለ <ፈልገህ አድነህ እራስህን አድን እና የ አዳምን መገኛ ፈልግ >አለው. እሱም ከ ኤፍራጠስ እና ጤግሮሰ ተነስቶ ቆ በትሩን ይዞ ሰና, አረርን, ባቢሎንን አልፎ ጋዛን መቀመጫው አርጎ ነበር. ከዛም ከጋዛ ወደ ግዮን ተጉአዘ አዛም ነበር ጌራም የተወለደው በዛ ነበር.
ወደ ግዮንም የመጣው 47 ነገስታት አስከትሎ ነበር መጀመሪያም መዝገበ ክበር (አክሱም ) ላይ ነበር ብዙም ሳይቆይ ወደ ዋልደባ ሄደ ቆ በትሩን ግሽ አባይ (የ አባይ መነሻ )ላይ አኖራት ወድያውኑ ቀስተ ደመና መቶ አዳኝ እንደ ናምሮድ ነው የሚል የ እግዚአብሔር ድምፅ መጣ እዛም መንግስቱን እንዲመሰርት ተፈቀደለት አይሞት የለ ሞተ ሞቶም የተቀበረው በ መዝገበ ክበር ነው.
ምንጭ ሀኪም አበበች አንድሮ ሜዳ ላይ ቀርበው እንደተናገሩት
✍️ ደሊላ

ከመጽሐፍት መንደር💠

06 Dec, 02:56


ምን ይሻላል?
ጓደኛዬ ሳይታሰብ ከሚስቱ ተጣልቷል።በምን መሰላችሁ ትላንት ታክሲ ሲሳፈር ፓኬት BANANA ማስቲካ አንድን ታዳጊ ለማገዝ ሲል ይገዛዋል።ልጁ ብዙም የማስቲካ ተጠቃሚ አይደለም። ይህንኑ ባህሪውን ሚስቱ ታውቃለች።እናም እቤቱ ሲገባ ኮሜዲኖ ላይ ያስቀምጠዋል።ሚስት ስታየው ታነሳና ውዴ ማስቲካውን አትፈልገውም አደል ልውሰደው ስትለው እሺ ይላታል ይዛው አጠገቡ ስትደርስ ከአምስቱ ሁለቱ ጎሏል።እንዴ በአንዴ ሁለት በልተህ ነው?ከመቼ ጀምሮ?ስትለው እሱ ነገር አለሙን ረስቶታል አይ ስከፍተው ታክሲ ላይ አጠገቤ አንዲት ልጅ ነበረች ያዢ ስላት አንዱን ወሰደችው ይላታል።የዚ ሰዓት ሚስት ሆዬ አራስ ነብር ሆነቻ። እሱ አልገባውም፤ብዙ ቆይቶ ነው የገባው።ለካስ አጅሬ ሚስቱንም የጠበሳት ታክሲ ላይ አውርቷት መውረጃዋ ሲደርስ እንደዚሁ በአጋጣሚ በያዛት ማስቲካ ልጣጭ ላይ ስልኩን ፅፎ ሰጥቷት ነው። እናም ይኽው ተበጣብጠውላችሁ ሽምግልናውን ለመምከር ለከሰዓት አንድ የከተማችን ታዋቂ ስጋ ቤት ሁለቱንም ቀጥሬአቸዋለሁ።እኔም እስከዛው ጋደም ብዬ "ሁኔታው ለኔ ተመቸኝ" የሚለውን ሙዚቃ እየሰማሁና እያሟሟቅኩ ነው።
ምንጭ :- FB መንደር

ከመጽሐፍት መንደር💠

05 Dec, 18:20


አያወራም ዝምተኛ ነው ፣ እንደሚወደኝ ነግሮኝ አያውቅም ፣ ሳጠፋ እነግርብሃለሁ እያሉ በእሱ ነው የሚስፈራሩልኝ ፣ እንዳላጠፋ ቀድሞ ይገስፀኛል  ፣  አጥና እያለ ያዘኛል።

ደብተር ካለቀብኝ ጠጅ ሊጠጣበት ያሰበውን ወይ ለባስ ብሎ ያስቀመጠውን ገንዘብ አልያም የእድር ክፍያውን አዛሎ ደብተር ይገዛልኝ ነበር ።

ሲያመኝ ከወትሮ በተለየ ይቆዝማል ፤ እንዴት ነህ እያለ ትኩሳቴን በእጁ ግንባሬ ላይ መዳፉን እየስቀመጠ ይለካል ፤ እናቴን አሁንም አሁንም ደህና ነው ምንም አይሆንም እያለ እየነገረ ራሱንም እሷንም  ያፅናናል ። ጠንከር ካለብኝ ጤና ጣቢያ ይወስደኛል

እያንዳንዱ እንቅስቃሴው ፣ ትኩረቱ ፣ ቁጣው ፣ ትዕግስቱ ፣ ግሳፄው ፍቅር እንደነበር ፤ ነገዬን ለመስራት ሲውተረተር ፣ ሲጨናነቅ ፣ ሲመታኝ ፣ ሲጨቃጨቅ እንደነበር ገብቶኛል

አባቴ ሆይ ያንተን ያህል ባይሆንም እኔም እወድሃለሁ
🙏
    ©
 

ከመጽሐፍት መንደር💠

04 Dec, 19:09


ትምህርት እንዲሆን ሀሳባችሁን በኮመንት ስር አስቀምጡ የአንዱ አጋጣሚ ለአንዱ ትምህርት ነውና👇👇👇👇

ከመጽሐፍት መንደር💠

04 Dec, 18:58


እንደተባሉት ያው ልጅ ቤቱን ከፍቶ ይዞቸው ወጣ፡፡ቀጥታ ከህንፃው በጎሮ በኩል ካለ እስካአሁን ካላዩት በአበቦች ያሸበረቀ የቅርጫት ኳስ ሜዳ ስፋት ያለው የተንጣለለ  የመዋኛ ገንዳ ያለበት ቦታ ነው የወሰዳቸው፡፡ ገንዳው ዳር ባለ በሰራሚክ ንጣፍ ባማረ ጎጆ የምግብ አይነትና፤ የመጠጥ አይነቶች ሞልተውበታል….ዙሪያውን መቀመጫዎች ሲኖሩ አስተናጋጅ መሰል ሁለት ሴትና አንድ ወንድ ዝግጅቱን ለማሳመር ከላይ ወደታች ይሯሯጣሉ፡፡ይዞቸው የመጣው ሰው ለገንዳው እይታ ምቹ የሆነ መቀመጫ ሰጣችውና ሶስቱም በተርታ ተቀመጡ፡፡
..በትካሻቸው ከባድ መሳሪያ የተሸከሙ ሰዎች በአከባቢ ራቅ ካለ ስፍራ በየተወሰነ ርቀት ፈንጠር ፈንጠር ብለው ሁኔታውን በጥንቃቄ ሲቃኙ ይታያል ፡፡ጥርት ካለው ከአማዞን ደን ሚነፍሰው ልስልና እርጥብ አየር ጋር አብሮ የሚነፍስ ጥኡም የላቲን ሙዚቃ እየተሰማ ነው፡፡በአካባቢው ሌላ ሰው የለም፡፡ድንገት ከገንዳው ብልቅ ብሎ ወደ ዳር የሚወጣ ሰው ተመለከቱ… ከእነሱ በ5 ሜትር  ርቀት ላይ ስለሆነ ማንነቱ ጥርት ብሎ ይታያቸዋል፡፡
ወደ ኑሀሚ በፈገግታ እየተመለከተ‹‹በሰላም ተመልሰሽ ወደቤትሽ በመምጣትሽ ደስ ብሎኛ››አላት፡፡
‹‹እንዴት አልመጣ ….ብጨክን ብጨክን ባንተ ጨክኜ መቅረት እችላላሁ››ብላ ምፀቱን በምፀት መለሰችለት…መልሷ በጣም አሳቀው፡፡
‹‹በጣም ናፍቀሺኝ ነበር….በህይወቴ እንደአንቺ ለማግኘት ያስቸገረኝ ሰው የለም….ድሮም ውድ ነገር ለማግኘት በጣም ከባድ መስዋዕትነት ይጠይቃል…ለማንኛውም መልካም ልደት ለሁለታችሁም…..ሰዎቹ  መሰናዶቸውን እስኪያጠናቅቁ ትንሽ ልዋኝ.. ከመሀከላችሁ መዋኘት    …የሚፈለግ ሰው ካለ ግን መጥቶ መወኘት ይችለል፡፡››ብሎ ወደገንደው መሀል እየዋኘ ሄደ፡፡
ምስራቅ ብድግ ብላ ልብሷን ማወላለቅ ጀመረች….ሁለቱም መንትያዎች ‹‹ሴትዬዋ አበደች እንዴ›› የሚል እይታ አፍጥጠው ያዮት ጀመር…፡፡
‹‹ፍቅር..ምን እየሰራሽ ነው››ናኦል ነው የጠየቃት…በእነዚ ሰው በላ አውሬ በሆኑ ሽፍቶች ፊት እርቃን ሰውነቷን ማሳየቱን ጥሩ ሆኖ አላገኘውም፡፡፡
‹‹ምን ነካችሁ ዛሬ እኮ የአናንተ ልደት ብቻ አይደለም..ጥምቀትም ጭምር ነው..ታዲያ ባገኘነው አጋጣሚ ብንጠመቅ ምን ይላችኃል?፡፡›› ብላ ጎንበስ በማለት ጫማዋን አወለቀችና ወለሉን እየነካካች ወደ ገንደው ተንቀሳቀሰች….ኑሀሚ ተነሳችና እሷ አንዳደረገችው ልብሷን በፍጥነት አወላለቀች.‹‹ሴቶቹ ጤናም የላቸው እንዴ››በማለት አልጎምጉሞ ባለበት መንቋራጠጡን ቀጠለ…ኑሀሚ ልብሷን አውልቃ እንዳጠናቀቀች ሄደችና ምስራቅ ጎን ቆመች…ዳግላስ ገንዳው መሀከል ባለ ከመነደሪ ላይ ተኝቶ ጭንቅላቱን በክንዱ ደገፍ በማድረግ አይኖቹን ሁለቱ እንሰት ላይ ተክሎ በገረሜታ ከሩቅ ይመለከታቸው…እንዲሁ ለማለት ያህል ጋበዛቸው እንጂ ያደርጉታል ብሎ አልጠበቀም ነበር…የኑሀሚን ሙሉ ተክለ ቁመና ሲያይ በሰውነቱ ሁሉ ሙቀት ተረጨና ውጥርጥር አለ…ለሳምንታት ሲያልመውና ሲመኘው የነበረው ገላ ይሄው በእሱ ቁጥጥር ስር ሆኖ ከፊት ለፊቱ እየታየው ነው….እሱ የእዚህ አካባቢ ገዢና አስተዳዳሪ ብቻ ሳይሆን የዚህ አካባቢ አምላክ ..ሁሉን አድራጊ..ሁሉን ፈጣሪ እንደሆነ ነው ሚያስበው፡፡፡
ኑሀሚ ምስራቅ ላይ ተለጥፋ ቆመችና ከንፈሯን በእጇቾ ከልላ‹‹ምን አቅደሽ ነው››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹ምን አቀድኩ››

‹‹ጫማሽን ምታወልቂ አስመስለሽ… ስለት ነገር ከወለሉ ላይ አንስተሸ ፓንትሽ ጠርዝ ላይ ስትወትፊ አይቼሻለው››
‹‹አይዞኝ አታስቢ የሰውዬውን ጉሮሮ አልበጥስብሽም››

‹አትቀልጂ…ሙከራችን በደንብ የታሰበበትና እና የሚያዋጣ መሆን አለበት…አትቸኩይ..››

ምስራቅ‹‹አታስቢ …አልኩሽ እኮ›› ብላ ተንቀሳቀሰችና ዘላ ገንዳ ውስጥ ገባች….ኑሀሚም ተከተለቻትና ገባች…ምስራቅ ወደግራ በኩል መዋኘቷን ስትቀጥል… ኑሀሚ ቀጥታ ወደ ዳግላስ መዋኘት ጀመረች….የምስራቅ እቅድ ዳግላስን መግደል ከሆነ ልታስቆማት ይገባል..አሁን ባሉበት ሁኔታ እሱን መግደል….የሚያመጣው ምንም ጥሩ ነገረ የለም..፡አነዛ አወሬ ታጣቂዎች በደቂቃዎች ውስጥ ቦጫጭቀው ይጥሏቸዋል…ከፋም ለማም ከሱ ጋር መደራደርና እሱኑ እለስልሰው ይዞው ትክክለኛው ጊዜ እስኪመጣ መጠበቁ የታሻለ እንደሆነ ታስባለች፡፡እና ወደእሱ የሄደችው ልትከላከልለት ነው፡፡
ስሩ ስትደርስ ‹‹እሺ ደግላስ ማለት የትኛው ነህ፡፡ስትል ጠየቀችው ፡፡

‹‹ማለት››

‹‹ዳግላስ ማለት አሁን አጠገቤ እዚህ አማዞን ደን መሀከል በነፀው ህንፃ ልዩ በሆነ ገንዳ ውስጥ እየዋኘ ያለው ነው ወይስ ከዛ ፔሩ ሊማ አግኝቼው ኤኪዬቶስ አንድ አልጋ ክፍል ውስጥ አብሬው ያደርኩት ሰው ነው››
‹‹ላንቺ ..የትኛው ቢሆንልሽ ትምርጫሽ››

ከመጽሐፍት መንደር💠

04 Dec, 18:57


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-31
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

የተወሰነ አርፈው ናፈቆታቸውን ካቀዘቀዙ በኃላ ናኦል‹‹እህቴ ዛሬ ቀኑን ታውቂያለሽ….››ሲል ግራ ያጋባትን ጥያቄ ጠያቃት፡፡
ወንድሜ ደግሞ መንጋትና መምሸቱን ካልሆነ በስተቀር እለቱና ቀኑኑ መለየት ካቀምኩ ቆየሁ…ለካ በህይወታችን ውስጥ ያሉ አብዛኛዎቹ ነገሮች በመከራ ቀኖቻችን ውስጥ ስንሆን ትርጉም አይኖራቸውም፡፡››
‹‹እንግዲያው ልንገርሽ ዛሬ ጥር 11 ነው …ልደታችን ነው፡፡››

ያልጠበቀችውን ዜና ነው የነገራት….መላ ሰውነቷን ነው የወረራት‹‹ኦ …ደሰስ ይላል…››መልሰው ተንጫጩ …..
ምስራቅ‹‹እናንተ ለምን እነዚህ አስተናጋጆቻችንን ጥቂት ውለታ አንጠይቃቸውም…››የሚል ድንገቴ ሀሰብ አቀረበች፡፡
‹‹ምን ››

ልደታችሁን  ለማክበር  የሚሆን  ጥቂት  ሻማ  …የተወሰነ  ከረሜላ  ካለ…ኬክም  ቢገኝ አንጠላም…ኮኬይንም  ቢያቀርቡልን ምስጋናችን ከፍ ያለ ነው…››አላች…ተሳሳቁ፡፡
‹‹ሌላውን አላውቅም.. ኮከይኑ ግን አይጨክኑብንም…..›› ምስራቅ ወደ መጥሪያው ሄደችና ተጫነችው…
‹‹እንዴት ፍቅር ምን ፈልገሽ ነው››ናኦል ምስራቅን ጠየቃት..ኑሀሚ ሁለቱንም አፈራረቀች ና       በገረሜታ ታያቸው ጀመር..ምስራቅ የእሷን ምልከታ ሳታስተውል ‹‹ትቀልዳላችሁ እንዴ.. ከመጠየቅ ደጅ አዝማችነት ይቃራል፡፡ሲባል አልሰማችሁም፡፡››በማለት በራፉ በድጋሚ ለማንኳኳት እጇን ስትሰነዝር  ….በድንገት በራፉ ተከፈተ…፡፡
ኑሀሚን ያመጣት ወጣቱ ልጅ ነው በራፉን የከፈተው…. የሚፈልጉትን ጠየቀችው፡፡ ‹‹ሀለቃዬን ጠይቄ ከፈቀደ የሚሆነውን አደርጋለው››ብሎ መልሶ በራፉን ዘግቶ ሄደ….፡፡ኑሀሚ ግን  በነበረችበት እንደፈዘዘች ነው፡፡
‹‹ምንድነው ያፈዘዘሽ››

‹‹የእኔ ፍቅር አለሽ እኮ…አንቺም ወዬ አልሺው ››

‹‹እና ›

‹‹እኔ እዚህ በአማዞን ጫካ ከአውሬውም ከሰው አውሬውም ለማምለጥ በመጣር ፍዳዬን በማይበት ሰዓት እናንተ ፍቅሬ ማሬ መባባል ጀመረችሁ››
‹‹ታዲያ በመሀከላችን ያለውን ለዘመናት የታፈነ ፍቅር ጭረን ካላቀጣጠልነው አንቺን ለመፈለግና ለማግኘት የሚያስችለንን ብልሀትና ጥንካሬ ከየት እናመጣን…. በነገራችን ላይ ያው አንቺ ወደ እዚህ እንደመጣሽ ሰሞን ነው የተጋባነው…››
‹‹የተጋባነው››

አዎ …ወዳሻንጣዋ ሄደችና የጋብቻ ሰርተ ፍኬታቸውን አውጥታ አሳየቻት…..ማመን አልቻለችም…ምስራቅ የሚያደርጉትን ሆነ የሚያወሩትን ሁሉ ሰዎቻቸው እየተመለከቷቸው እንደሆነ ታውቃለች….የጀመሩትን ማስመሰል አስከወዲያኛው መቀጠል አለባቸው….አዎ ከዚህ እስኪወጡ ከናኦል ጋር ባልና ሚስቶች ናቸው….ከወጡስ በኃላ አንዴት ይሆናል የሚለውን እርግጠኛ አይደለችም…..ልጁን በፊት ከምትወደው በተለየ መንገድ ወዳወለች…..ጠረኑ ክፉኛ ለምዳዋለች…..ፍቅሩ ልቧ ውስጥ እየተንጠባንጠበ ነው…..ይሄንን የጋብቻ ሰርተፍኬት እንደቀልደ በቃ አሁን ጉዛችን አበቅቶለታል ብላ ቀዳዳ የወረቀት ቅርጫት ውስጥ ለመክተት ጥንካሬው መቼም ቢሆን የሚኖራት አይመስላትም፡፡
ከተረጋጉ በኃላ ኑሀሚ ሰውቷን ለመታጠብ ፈለገች እና ወደሻወር ቤት ገባች፡፡ታጥባና ነፅታ ስትወጣ ክፍላቸው ውስጥ የተለየ ነገር ነበር የጠበቃት….በርከት ያሉ የሴት ቀሚሶች እና ሙሉ የወንድ ሱፍ ሱሪ የያዘ ተሸከርካሪ የልብስ መደርደሪያ ወለሉ መሀከል ላይ ተቀምጦ ናአልና ምስራቅ ፊት ለፊቱ  ቆመው በአድናቆት እየተመለከቱት ደረሰች፡፡
ያገለደመችውን ፎጣ በደንብ አጥብቃ አሰረችና ‹‹ምንድነው ይሄ››ስትል ጠየቀች፡፡

‹‹ይህን ያመጣው ልጅ..በጠየቃችሁት ጥያቄ መሰረት ልዳታችሁን ለማክበር ተፈቅዷል…..ከዚህ የሚሆናችሁን ልብስ መርጣችሁ ልበሱና ልደቱ ወደሚከበርበት ቦታ ከ30 ደቂቃ በኃላ መጥቼ ወስዳችኃላው›› ብሎል፤ብለው አስረዷት፡፡
‹‹አንቺ ሰዎቻችን ደግ ናቸው…….መጀመሪያ በደንብ አስደስተውን የምንፈልገውን ነገር እንድናደርግ ከፈቀዱልን በኃላ ከዛ አመስግነናቸው እንድንሞት ነው የፈለጉት፡፡››አለች ምስራቅ፡፡
‹‹እሱስ ቢሆን ማን አየበት  ይመስገን ነው››….ብላ ካመጣጡላቸው ቀሚሶች መካከል ለእሷ
የሚሆናትን መምረጥ ጀመረች….በሀያ ደቂቃ ውስጥ ሶስቱም ልክ እቤተ-መንግስት ከንግሱ ጋር የእራት ግብዣ እንዳላባቸው መኮንንቶች ሽክ ብለው ዘንጠውና አምረው በቀጣይ
የሚሆነው መጠበቅ ጀመሩ፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

01 Dec, 18:48


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-30
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ኮሎምቢያ/አማዞ ደን ማህፀን ውስጥ
ካርሎስ በተሰበረ ልብ ምርጫ አልባ ሆኖ በህይወቱ የመጨረሻውን ፍቅር ያፈቀራትን ይቺን ጠይም ኢትዬጵያዊ ሴት ሳይወድ በግድ ከማናአስ ወደ ቲጎና በፕሌን… ከዛ ደግሞ በጀልበ ከብራዚል ድንበር ወደኮሎምቢያ አሻግሯትና ላቲሲያ ከተማ ጫፍ ድረስ ሸኛት፡ከዛ እሱ ከዳግላስ የንፍስ ጠላቶች ጋር ለመደራደር ደቡብ ምእራብ ኮሎምቢያ ድንበር ተጠግታ ወደምትገኘው የቪንዚዎላዋ ሳና-ካርሎስ ከተማ ጉዞ ጀመረ …፡፡
ይህቺን ያፈቀራትን አፍሪካዊ ሴት ማዳን ማለት እራሱን ማዳን ማለት ነው፡፡ሰው እራሱን ለማዳን ደግሞ ምንም ያደርጋል፡፡ዳግላስን ያገኙትን ማንኛውንም አጋጣሚ ተጠቅመው ሊያጠፉት የሚፈልጉ የቢዝነስ ተፎካካሪዎች እንዳሉት ያውቃል..እሱ ደግሞ ስለ ዳግላስ የቢዝነስ ሚስጥሮች ፤ መግቢያ መውጫውን ፤ድክመትና ጥንካሬውን በደንብ ያውቃል…አሁን የሚያገኛቸው ሰዎቹ ደግሞ ሃይልና ብር አላቸው….እነሱ እሱን አምነውት ከተቀበሉትና አብረውት ለመስራት ከወሰኑ ዳግላስን እስከወዲያኛው አስወግዶ ኑሀሚንና ወንድሟን ነፃ ለማውጣት የሰለለችው ቢሆን ተስፋ አለው፡፡ያ ተስፋ ካልተሳካ ነፍሱን እንደሚያስከፍለው ያውቃል…ቢሆንም ግድ የለውም…ያቺ የሰለለች ተስፋ ከመቶ አንድ ፐርሰንት ብትሆንም እንኳን  ከመሞከር ወደኃላ አይልም..ለዛ ነው እሷን ወደዳግላስ ልኮ እሱ የዳግላስን ጠላቶች አግኝቶ ለመደራደር ጊዜ ሳያባክን ጉዞ የጀመረው፡፡
ኑሀሚ ካርሎስ እንደነገራት ላቲሲያ ከተማ በተቀመጠችበት ሆቴል ነው አንድ ሰዓት እንኳን ሰትቆይ የዳግላስ ሰዎች በቁጥጥር ስር ያዋሏት፡፡በመጀመሪያ እዛ ላቴሲያ ከከተማው ወጣ ብሎ አማዞን ወንዝ ደር ካለ ወደ አንድ  ሰዋራ ቤት ነበር የወሰዷት፡፡ለአራት ቃናት ያህል እዛው አስቀመጧት፡፡በየቀኑ የሚያስፈልጋትን ያህል ምግብ ፤ልብስ እና መጠጥ ያቀርቡላታል፡፡ግን ማንም ሊናግራት የሚደፍር ፤ብታናገራቸውም የሚመልስላት አልነበረም፡፡በየቀኑ ምግብ እና መጠጥ እንዲሁም የሚያስፈልጋትን ነገር የሚያመጡ ሁለት ሰዎች አሉ….መጥተው እቤቱ ጠረጴዛ ላይ አስቀምጠውላት ይሄዳሉ….ብታናግራቸው አይመልስላትም፡፡ጠባቂዎቾ እርስ በርስም ቁጥብ ቃላትን ሲለዋወጡ ብትሰማ እንኳን በማይገባት ቋንቋ ስለሆነ ምንም መረዳት የምትችለው ነገር አልነበረም ፡፡ይበልጥ ልትቆጣጠረው የሚከብዳት ጥልቅ ድባቴ ውስጥ እየገባች መጣች፡፡እሷ ካለችበት ቤት አስር ሜትር እርቃ ባለች ጎጆ አንድ ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ ጎረምሳ ሁሌ ንቁ ሆኖ ሲጠብቃት  ታየዋለች…ወደእሷ መጥቶ ለማውራት   አይሞክርም…እሷም ወደእሱ ለመቀረብ ምንም ጥረት ኣላደረገችም፡፡ይህን ጠበቂ ወይ ጥላው ወይ ገድላው በቀላሉ ማምለጥ እንደምትች ታውቃለች…..ግን ያ አይደለም እቅዷ፡፡ አሁን ሂጂ አምልጪ የሚላት አዛኝ ሰው ቢኖር እራሱ እሺ ምትልበት ሁኔታ ላይ አይደለም ያለችው፡፡አሁን የእሷ ጥረት ወደፊት ስምጥ ወደሆነው የአማዞን ደን ማህፀን ውስጥ ገብቶ ወንድሟን ማግኘት ነው…ምንም ያህል ዋጋ ቢያስከፍላት ግድ የላትም፡፡እንደው ወንድሟንና ምስራቅን የማትረፍ እድሉ ባይኖራት እንኳን የዩትን መከራ አብራ አይታ የሚጎነጩትን ሞት አብራ ለመሞት ነው ፅኑ ፍላጎቷ፡፡
እርግጥ ካርሎስ እንዳላት ከዳግላስ ጠላች ጋር በማበር ስለእሱም ሆነ ስለድርጅቱ… ስለሚኖርበት አከባቢና ..ስለግዛቱ የሚያውቀውን መረጃ ሁሉ በመስጠት እሱን እንዲያወድሙትና በዛ ግረግር መካከል እሷን ከወንድሟ እና ከምስራቅ ጋር ሊያስመልጣቸው የተቻለውን ሁሉ እንደሚጥር ቃል ገብቶላታል….ደግሞ የገባውን ቃል ለማክበር የተቻለውን ያህል እንደሚጥር እርግጠኛ ነች…ምን አልባትም በእነዚህ አራት ቀኖች የሚፈልጋቸው ሰዎች ጋር ተገናኝቶ እቅድ እየነደፈ ይሆናል፡፡
አሁን እሷን የጨነቃት እስከመቼ እዚህ አፍነው እንደሚስቀምጧት ነው..የመጨረሻ ተሰላቸች፡፡ እና የሆነ ነገር አድርጋ ትኩረታቸውን ማግኘት እንዳለባት እና ትኩረታቸውን ለማግኘት ደግሞ እንሱን ማበሰጨት አንድ ዘዴ እንደሆነ አመነች፡፡ውጭ እሷ እንድታመልጥ ሳይሆን ከውጭ ሌላ ሰው መጥቶ እሷ ላይ ጥቃት እንዳያደርስ ጥበቃ እያካሄደ የሚመስለውን ወጣት ልታጠቃው እቅድ ነደፈች፡፡ከልተፈታተናት ላትጎዳው ወስናለች…..አፀፋዊ ምላሹ ጠንካራ ከሆነ ግን ቢሞትም ግድ የላትም…፡፡
ዝም ብላ ካለወትሮዋ ወደእሱ ተንቀሳቀሰች፡፡መሳሪውን አዘቅዝቆ እንደያዘ ባልተለመደ እንቅስቃሴዎ ግራ ተጋብቶ አፍጦ እያያት ነው፡፡ቀረበችው፡፡ በመሀከላቸው ያለው ርቀት ሁለት ሜትር ብቻ ሆነ፡፡ወስና እግሯን ልታወናጭፍ ስትል ከወደ በራፉ ብዛት ያለው የእግር ኮቴና ድምፅ ሰማችና ባለችበት ተረጋግታ ቆመች፡፡ፊቷን አዙራ ስታይ እውነትም ሶስት የሚሆኑ የታጠቁ ግሰበች ናቸው ..ወደ እነሱ እየመጡ ነው፡፡ ፊት ለፊቷ በቆመው ልጅ እድለኝነት ተገረመችና ፈገግ አለች፡፡
ወዲያው ነበር አፋፍሰው ይዘዋት የወጡት፡፡የ 20 ደቂቃ የእግር መንገድ ካስኬዷት በኃላ ወንዝ ዳር አካባቢ ደረሱ፡፡ወዲያው ጀልባ ላይ ነው ይዘዋት የወጡት…ከዘ በኃላ ለአንድ ሰአት ተኩል ያህል ከጀልባ  አልወረዱም..አሰልቺ የሆነ ጉዞ ነበር የተጓዙት፣ከዛ ባልጠበቀችው ሁኔታ እዛ ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ሚኪና ነው የጠበቃት፡፡አንከውክወው መኪናው ውስጥ አስገቧትና ጥቁር ጨርቅ በጭንቅላቷ አጥልቀው አንገቷ ድረስ በማልበስ ሙሉ በሙሉ እይታዋን ከለሉት፡፡ በጥቅጥቅ ደን ውስጥ የእግር መንገድ በምትመስል ቀጭን መንገድ ጫካውን እየሰነጠቁ፤አውሬዎችን እያስደነበሩ፤ለሁለት ሰዓት ያህል ይዘዋት ተጓዙና  ድንገት የመንገዳቸው መጨረሻ ደረሱ፡፡መኪናዋ እንደቆመች የተሸፈነችበት ፅልመታዊ ጥቅር ልብስ ከጭንቅላቷ ላይ ገፈው አነሱላት፡፡ወዲያው ከአካባቢው ብርሀን ጋር እራሷን ማሳማማት አልቻለችም…ብዥ አለባት፡፡ቀስ እያለች ዙሪያ ገባዋን ማየት ስትችል እዛ ደን ውስጥ ይገኛል ብላ ያልጠበቀችው  አንድ ግዙፍ ግቢ ከፊተ ፊቷ ገጨ ብሎ አየች፡፡እንድትወርድ በምልክት ነገሯት፡፡ ወረደች፡፡ውስጧን በደስታ ተጥለቀለቀ…አዎ ቦታው እራሱ ነው፡፡ወንድሟና ምስራቅ ጎን ለጎን ሆነው እዚህ ስፍራ የተነሱትን ፎቶ ነው የላከላት…ወንድሟን ልታገኝ በመሆኑ ተደስታ እግሮቾን በአየር ላይ አድርጋ ዘለለች ፡፡
ይዘዋት ከመጡት መካከል አንዱ በተሰባበረ እንግሊዘኛ እንድትከተለው ነግሯት ወደዋናው ቤት ይዞት ሄደ.፡፡አንደኛ ፎቅ ላይ እንደወጡ አንድ ልጅ እግር ወጣት ተቀበላትና ታጣቂውን አሰናብቶ እሷን ይዞት ወደውስጥ ገባ፡፡ግዙፉን ሳሎን እየሰነጠቁ አለፉ… የተወሰኑ ኮሪደሮችን ከለፉ በኃለ የሆነ ክፍል ጋር ሲደርሱ ቆመና ከኪሱ ቁልፍ አውጥቶ መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹እናንተ ሰዎች ያማችኃል እንዴ..አሁንም ክፍል ውስጥ አስገብታችሁ ለተጨማሪ ቀን ለትቆልፉብኝ ነው…ወንድሜን እንድታገናኙኝ አፈልገለሁ…ለሀለቃህ ለዳግላስ ንገረው… ወንድሜን አገናኘኝ ብላለች በለው….አሁኑኑ ንገረው››

ከመጽሐፍት መንደር💠

01 Dec, 12:52


ለሁልጊዜዋም ለምርጧ እናታችን
❤️‍🔥❤️‍🔥❤️‍🔥❤️‍🔥❤️‍🔥❤️‍🔥❤️‍🔥❤️‍🔥
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal
https://t.me/manbabemulusewyaderegal

ከመጽሐፍት መንደር💠

28 Nov, 10:15


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-28
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ካርሎስና እና ኑሀሚ በአምስተኛ ቀናቸው ነበር ከአከባቢው የተንቀሳቀሱት፡፡በዛን ወቅት ኑሀሚ የተመረዘችው መርዝ ሙሉ በሙሉ ከሰውነቷ ተወግዶ… የሟሸሸ የነበረም ሰውነቷ ተነቃቅቶ….ጥንካሬዋም በተወሰነ ፐርሰንት ተመልሶ ነበረ፡፡ ባለውለታቸውን የሆነችውን ጎጆ በፍቅር ተሰናብተው አካባቢውን ለቀው የአማዞንን ወንዝ ደርቻ ተከትለው በምስራቅ አቅጣጫ ለአንድ ሰዓት ተኩል በእግር ከተጓዙ በኃላ አንድ እሮጌ ጀልባ የያዘ ግለሰብ አጋጠማቸው፡፡ከእሱ ጋር በገንዘብ ተደራደሩና ታብቲንጋ ከተማ ድረስ እንዲያደርሳቸው ተስማምተው ጉዞ ጀመሩ፡፡የዛኑ ቀን አመሻሽ ላይ ያሰቡበት ቦታ ደረሱ፡፡
‹‹ይህቺ ከተማ የአየር ትርንስፓርት አገልግሎት አላት ነው ያልከኝ..?››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹አዎ አላት..ማኑሳ ድረስ መሄድ ይቻላል፡፡››
‹‹ታድለን…በቃ ነገሮች ወደመጨረሻው ምዕራፍ እየተቃረበ ነው ማለት ነው…ተዲያ ወደከተማው እንግባና የአየር ትኬት ካገኘን እንሞክራ››
‹‹አይ ወደከታማ መግባት አንችልም..፡፡እንደምታያት ይህቺ አንስተኛ የጠረፍ ከተማ ብራዚል ውስጥ ትገኝ እንጂ ለኮሎምቢያ ቅርብ መሆኗን እንዳትረሺ..ያ ማለት ደግሞ የዳግላስ ተፅእኖ በተወሰነ መልኩም ቢሆን ይኖራል ማለት ነው፡፡ በተለይ ወደ ብራዚል ከገባን ቀጥታ የአየር ትራንስፖርት የሚገኝባት ከተማ ይህቺ ስለሆነች ቀጥታ ወደእዚህ እንደምንመጣና ወደአየር መረፊያ ጎራ እንደምንል በቀላሉ ይገምታል..ስለሆነም ከተማው ውስጥ ዋና ዋና ቦታዎች እና በተለይ ደግሞ አየር ማረፊያ ላይ ሰዎቹን እንደሚያስቀምጥ እርግጠኛ ነኝ፡፡
‹‹እና ምን ይሻለናል?፡፡››በስጋት ጠየቀችው፡፡
‹‹ረጅሙን መንገድ ነው የምንመረጠው..ማለት አሁንም ወደ ምስራቅ ጉዞችንን እንቀጥልና ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ ነው የምንሄደው፡፡››
‹‹ቤንጃሚን ኮንስተንት ደግሞ ማን ነች?››
ቤንጃሚን ኮንስተንት አማዞን ደን ውስጥ ከበቀሉ የብራዚል የጠረፍ ከተሞች ውስጥ አንዷ ስትሆን ከተማዋ ጃዋሪ በተባለ ወንዝና በአማዞን ወንዝ ተከባ የምትገኝ ትንሽ ከተማ ነች፡፡ከዚህ አሁን ካለንበት ከተማ በጀልባ የሁለት ሰዓት ቢፈጅብን ነው፡፡ማንም ወደ ዛች ከተማ ይሄዳሉ ብሎ እይገምተንም…እዛ ከደረስን በኃላ የተሻለ የተባለ ዘመናዊ ጀልባ እንከራይና ቀጥታ ወደ ማናአስ እንጓዛለን፡፡
‹እንዳልክ …ግን የሆነ ቻርጅ ያለበት ቦታ ፈልግን ስልኬን ቻርጅ ማድረግ አለብኝ፡››የምታስበውን ነገረችው፡፡
‹‹ምን ሊያደርግልሽ?››
‹‹ትቅዳለህ..ለወንድሜ ደውዬ ቢያንስ እስከሁን በጤና መሆኔን ላሳውቀው ነዋ፡፡››
‹‹አይ አይሆንም…ስልክሽን አብርተሸ ለወንድምሽ ደወልሽለት ማለት ያለሽበትን አካባቢ ቀጥታ ለሀገርሽ መንግስት እናም ጉደዩን ለሚከታተሉ ለአካባቢው መንግስታት አሰወቅሽ ማለት ነው..ያ ሆነ ማለት ደግሞ ዳግላስም በቀላሉ ዜናውን አገኘ ማለት ነው፡፡እና ሁሉም እኛን ለማግኘት በአካባቢው አሰሳ ይጀምራሉ…ከዚህ በፊት እንዳለኝ ልምድ ደግሞ ከየትኛውም መንግስት ቀድሞ ደጋላስ አፈፍ እንደሚያደርገን እርግጠኛ ነኝ››
‹‹እና ምን ይሻላል?››
‹‹የሚሻለውማ..ማናስ እስክንገባ መቻል….ነው…ወንድምሽም ዘላለም ከሚያጣሽ…ስድስት ሰባት ቀን በናፍቆት እና በትካዜ ቢሰቃይ ይሻላል፡፡አሁን አንቺ እዚሁ አካባቢ እራስሽን ከሰው እይታ ከልለሽ ትጠብቂኛለሽ… እኔ እራሴን ለውጬ ከታማ ገብቼ እመለሳለሁ››
‹‹እንዴ… እኔን እዚህ ብቻዬን ጥለኸኝ ምን ትሰረለህ?››
እጁን ወደኪሱ ሰደደና የሆነ መሀረብ አውጥቶ ቋጠሮውን ፈታና ሁለት የጨው አንኳር የሚመስል አብረቅራቀ መአድን አነሳና በእጇ መዳፍ ላይ አስቀመጠ፡
‹‹ምንድነው?››በመገረም እያየች ጠየቀችው፡፡
‹‹እንቁ ነው..በደኑ ውስጥ በአጋጣሚ በስራ ላይ እያለው በእጄ የገባ ነው..እንደዚህ አይነት ንብረት በምንም አይነት ሁኔታ ቢሆንም በእጅ ከገባ ለገዛ ጥቅም ደብቆ መስቀመጥ በሞት የሚያስቀጣ አደገኛ ወንጀል ነው..በወቅቱ ለዳግላስ ማሰረከብ ነበረብኝ…እኔ ግን ደመነፍሴ አንድ ቀን አጣብቂኝ ውስጥ ስገባ  ይጠቅምሀል ብሎ ሹክ ስላለኝ..የመጣው ይምጣ ብዬ ደብቄ አስቀምጬው ነበር፣.እና አሁን ወደከተማ ሄጄ ወደገንዘብ ልቀይረው...እረጅም የጀልባ ጉዘ ስለሚጠብቅ ብዙ ገንዘብ ያሰፈልገናል…››
መጀመሪያ እንቁውን መለሰችለት..መልሶ በመሀረቡ ቋጠረውና ወደኪሱ ከተተው..፡፡
ከሷ የእጅ ቦርሳዋን አነሰችና ዚፕን ከፈተች፣ከላይ ያሉትን እቃዎች አወጣች ፡፡ፊቱን አዙሮ ሊሄድ ሲል ከስር እንደታሸገ የተቀመጠውን ዶለር መዥርጣ አወጣችና እጁ ላይ አስቀመጠችለት፡፡
‹‹ይሄ አይበቃም?››
አይኖቹ በመገረም ደመቁ‹‹አንቺ ይሄን ሁሉ ብር ከየት አመጣሽ?››
የዛሬን አያድርገውና ሀለቃህ ዳግስ ነበር የሰጠኝ..እና አይበቃም›››….ብላ እንዴት እንዳገኘች ታሪኩን አስረዳችው
‹‹ትቀልጂያለሽ እንዴ..ይሄ እኮ በጣም ብዙ ብር ነው….በይ አሁን ጀልበ እንፈልግ››አለና ብሩን መልሶላት ቦርሳ ውስጥ ከከተተ በኃላ ተያይዘው ወደፊት ለፊት መራመድ ጀመሩ፡፡
እንደተነጋገሩት እዛው አድረው ንጊት ላይ ወደ ቤንጃሚን ኮንስተንት ከተማ በጅልባ ተጓዙ፡፡ እዛ አንድ ሰዓት ብቻ በማሳለፍ ሌላ ዘመናዊ የተባለ ጀልባ ተከራዩና ወደአማዞኒያ ግዛት ዋና ከተማ ማናአስ ጉዞ ጀመሩ፡.ያው ጉዞ ቀላል አልነበረም….6 ቀን ነው የፈጀባቸው ፡፡ግን ደግሞ በህይወት ረጅም ዘመን ለመኖር ስድስትና ሰባት ቀን መስዋት ማድረግ ያን ያህል ክፉ የሚባል ስላልሆነ አላማረረችም ፡፡
…ታብቲንጋ….ሳኦ ፍረንሲስኮ…ኮረንቲዛ….ዲ አማተራ…ሳኦ ዶሚንጎ….ሳንታ አንቶኒኦ….ሳኦ ፍሊክስ… ሳንታ ሉዚያ… የመሳሰሉን አያሌ ታዋቂ ቦታዎችንና የኣማዞን ወንዝ ዳር ከተሞችን አቋርጠው ማናአስ ከተማ ደረሱ ፡፡
ማናአስ(Manaus) በሀገረ ብራዚል የኣማዞኑያ ግዛት ዋና ከተማ ነች፡፡በብራዚል 2.2 ሚሊዬን ኑዋሪዎች የሚኖሩበት 7ተኛው ትልቋ ከተማ ስትሆን ከተማዋ በአማዞን ደን ውስጥ ከተቆረቆሩ ከ1 ሚሊዬን በላይ ኑዋሪዎች ካሏቸው ሁለት ትልልቅ ከተሞች መካከል አንዶ እና ዋነኛዋ ነች.››
በዛ ላይ የአማዞን ደንን እና የአማዞን ወንዝን ሚስጥር ለመበርበር እና ጥናት ለማጥናት ከመላው አለም የሚሰባበሰቡ ሳይንተስቶችና ተመራማሪዎች በዋናነት የሚከትሙባት ከተማ ነች፡፡በዚህ የተነሳ የአማዞን ልብ የሚል ቅፅል ስም ይሰጧታል፡፡በተጨማሪ አንዳንዶችም የትርፒካሎ ፓሪስም እያሉ ያሞካሻታል፡፡
ማናአስ  ከተማና አካባቢው በኬሚካል ፕሮጀክት..በለውዝ ምርት ….በሳሙና ምርት….በመርከብ ግንባታ እና በጎማ ተክል ምርት በጣም የታወቀች ነች፡፡፡በተለይ በጎማ ምርት ከ1800 አመት በፈት ጀምሮ የታወቀች በመሆኗ ከሀገሪቱ ሀብታም ከተሞች ግንባር ቀደሞ እንድትሆን አስችሏታል፡፡ማናአስ ከተማ በ2014 እ.ኤ.አ የአለምን ዋንጫ ካስተናገዱ 12 የብራዚል ከተሞች አንዷ እንደሆነች ይታወቃል፡፡በከተማዋ ምስራቅ አቅጣጫ ድፍርሱ የኒግሮ ወንዝ እና ሰማያዊው የሶሊመስ ወንዝ አንድ ላይ ተቀላለቅሎ ወደአማዞን በገባርነት የሚፈስባት ልዩና አስደማሚ ስፍራንም በመደመም ማየት ይቻላል፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

27 Nov, 11:49


#ማነው_ጥፋተኛው?
(ከናይጀሪያን ፔጅ የተወሰደ)

ሰውዬው አገር ሰላም ብሎ ወደ ቤቱ ሲመጣ ሚስቱ ከወንድ ጋር ስትማግጥ እጅ ከፍንጅ አገኛት። ባልሆዬ ሚስቱን ያማገጠበት ሰው ጋር ድብድብ እንደመፍጠር፣ ነገር አለሙን ችላ ብሎ ወደ ሳሎን ተመለሰና መፅሃፍ ቅዱሳዊ ቪዲዮ ማየት ጀመረ።

ወይዘሮ ሚስትና ውሽሜ በከፍተኛ ፍርሃት እየተንቀጠቀጡ ነው።

ውሽሜ እንደምንም ልብሱን ለባበሰ እና ወደ ሳሎን መጥቶ እየተንተባተበ ወንጀሉን መናዘዝና ይቅርታ መጠየቅ ጀመረ። አባዋርዮው ግን ፍፁም በተረጋጋ ስሜት "ችግር የለውም በህይወት ውስጥ ሊከሰት የሚችል ፈተና ነው፤ መሄድ ትችላለህ" ሲል አሰናበተው። ሰውዬውም በፍርሃት እየተንቀጠቀጠ ወጥቶ ሄደ።

ሚስትዮዋ የመኝታ ሰዓት እስኪደርስ ከመኝታ ቤት አልወጣችም ነበር።

ባልዮው ቲቪውን አጠፋፋና ወደ መኝታ ቤቱ ገብቶ ያ መጥፎ ድርጊት የተፈፀመበት አልጋ ላይ ብርድልብሱን ተጠቅልሎ ተኛ።

ሚስትዮዋ ወለሉ ላይ ተቀምጣ እየተንሰቀሰቀች ታለቅስ ነበር። ባልዮው ምንም ነገር አልተናገራትም፣ አልጠየቃትምም።

ጠዋት ከእንቅልፉ ሲነቃ ሚስቱን ሞታ አገኛት። ራሷን በራሷ አጥፍታለች። ፖሊስ ግን ባልዮውን በወንጀል ድርጊት ጠርጥሮ በቁጥጥር ስር አዋለውና ጭራሽ በነፍስ ማጥፋት ወንጀል 20 ዓመት እስራት ተፈረደበት።

#ጥያቄ: በዚህ ሂደት ውስጥ ኢፍትሃዊነት የተንፀባረቀው በማን በኩል ነው

1.ባል
2.ሚስት
3.ህጉ እራሱ?

(ሃሳብ አስተያየት ስጡበት፣ እንወያይበት)
___//_____
መልካም ቀን🙏🙏🙏🙏🙏🙏

ከመጽሐፍት መንደር💠

25 Nov, 18:38


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-27
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ
///
እቤት ውስጥ ከገብ በኃላ እንኳን ናኦል እና ምስራቅ  ለረጅም ደቂቃ ደንዝዘውና ፈዘው ማህል ወለል ላይ በዝምታ ተገትረው ነበር።

ናኦል እንባ እየተናነቀው"ምስራቅ ምን ውስጥ ነው የገባነው..?ይሄ ሰውዬ ተጫወተብን"አላት ።
ምስራቅም ወደእሱ ተንደረደረችና  አቀፈችው ።አንገቱ ስር ሽጉጥ ብላ በጆሮው "አትደንግጥ...እቅድ አለኝ"አለችው።

ዝም አለ...ከዚህ ለመውጣት ምን አይነት ተአምራዊ ዕቅድ ሊኖራት እንደሚችል ምንም ሊገለፅለት አልቻለም።ቢሆንም ከሞስራቅ ጋር ባሳለፋቸው በርካታ አመታት ብዙ ተአምር መሳይ ነገሮችን ስትከውንና ደጋግሞም ሲሳካላት ታዝቦልና የተናገረችው ነገር ንቆ ሊያልፈው አልደፈረም።...
ብራዚል/አማዞን ደን ውስጥ
አካባቢው ድቅድቅ ጨለማ ነው፡፡ጨረቃዋም በሰማይ ላይ ብርሀን አልፈነጠቀችም፡፡ከዋክብቱም የከሰሙ መስለዋል ፡፡ኑሀሚ ካርሎስ የሰራላት የአንጨት ርብራብ አልጋ ላይ ተኝታ የእጇ ጥዝጣዜ ታዳምጣለች፡፡እርግጥ ከትናንቱ የተሻ ጤንነት ላይ ብትገኝም ሰውነቷ ግን ሙሉ በሙሉ እደዛለ ነው፡፡በህይወቷ በእንዲህ አይነት ደካማንትና አቅመ ቢስነት ተሰምቷት አያውቅም፡፡ ካርሎስ በሶስት ቀን ውስጥ ሙሉ በሙሉ እደምታገግም ነግሯት ነበር ፡፡ አሁን አሁን ያለችበት ሁኔታ ስታስበው በሶስት ወር ተሽሏት ከዚህ አካባቢ የምትንቀሳቀስ እየመሰላት አይደለም፡፡ያም ሆኖ ግን ትናንትና ጉሮሮዋን ፈጥርቆ ነፍሷን ሊነጥቃት የነበረው ሲኦላዊ ህመም ዛሬ በሙሉ አቅሙ የለም፡፡ያ የሆነው ደግሞ ካርሎስ እጇ ላይ ባሰረለት የባህል መድሀኒት ምክንያት ነው፡፡
እንደምንም አንገቷን ወደ ዳር ሸርተት አድርጋ አየችው፡፡ እዛው ርብራብ አልጋ ጎን ባለ ጠፍጣፍ ድንጋይ ላይ ተቀምጦ አንገቱን በካኔቴራው ሙሉ በሙሉ ሸፍኖ የእንጨት አልጋውን ቋሚ ተደግፎ ጨልጥ ያለ እንቅልፍ ተኝቷል፡፡ አሳዘናት፡፡ቢቻላት ኩርምት ብሎ በተቀመጠበት እንቅልፍ የወሰደውን ይሄን መልካም ሰው ጎትታ ወደራሷ ስባ እሷ የተኛችበት የእንጨት ርብራብ ላይ ከጎኗ ሽጉጥ አድርጋው ብትተኛ ደስ ይላት ነበር ፡፡
ወዲያው ሀሳቧን ሳትጨርስ ነጎድጓድ በሰማዩ አንፀባራቂ ብርሀን እየረጨ ያንቧርቅ ጀመር፡፡የሚያስፈራ ደራጎናዊ ድምፅ አካባቢውን ያናጋው ጀመር፡፡ ኑሀሚ እንኳን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እንደዚህ አይነት ቦታ ሆና ይቅርና በሀገሯ ሰማይ ስር በገዛ ቤቷ እያለች ሳይቀር እንዲህ አይነት ነጎድጎድ በጣም ነው የሚያስፈራት፡፡፡እንደምንም ደካማ እጃን አንቀሳቀሰችና ትከሻው ላይ አኑራ በመወዝወዝ..‹‹ካርሎስ ካርሎስ›› ስትል ጠራችው፡፡

በርግጎ ተነሳ‹‹..ምን …አመመሽ እንዴ?››
‹‹አይ ነጎድጎድ ፈራለሁ››
ከተቀመጠበት ተነሳና ወደእሷ ተንቀሳቀሰ….ርብራቡ ጠርዝ ላይ ከጎኗ ተቀመጠና እጆቿን በእጆቹ ውስጥ አስገብቶ ያሻሽላት ጀመር፡፡ከእሱ ሰውነት ወደእሷ እየተላለፈ ያለው ሙቀት ብቻ ሳይሆን ብርታትና ጥንካሬ ጭምር ነው፡፡
በድጋሚ‹‹በጣም እኮ ነው የፈረሁት››አለችው፡፡
‹‹አይዞሽ…ስጋታችን፤ፍረሀቶችንና እና ጥርጣሬዎቻችን ሰው በመሆናችን የተሰጡን ፀጋዎች ናቸው፡፡ካለበለዚያማ እህያና በቅሎ መሰል አይነት ስሜቶች ስለሌላቸው ከእኛ የተሻሉ እደለኞች ናቸው ልንል መሆኑ ነው?፡፡››
‹‹እሱስ እውትህን ነው››አለችና ይበልጥ ተለጠፈችበት

ወዲያው ሰማዩን አግቶ ይዞ የነበረውን ዝናብ ዘረገፈው፡፡የተሰራችው ጊዜያዊ ጎጆ ሙሉ በሙሉ በዛ ድቅድቅ ጨለማ የሚወርደውን የዝናብ ውሀ አግዳ ለማስቀረት ጥንካሬው አልነበራትም፡፡ሁለቱም በ5 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በዝናብ ራሱ፡፡እሷ ከህመሙና የሰውነት ጥንካሬዋ በመዳከሙ የተነሳ ዝናቡንና ቅዝቃዜውን መቋቋም ስላልቻለች ትዘፈዘፈች፣ካርሎስ የሚያደርገው ጠፋበት፡፡ ሙሉ በሙሉ ወደእንጨት አልጋው ወጣና ከእሷ ተስተካክሎ ተኛ…አቀፋትና ወደራሱ አስጠግቶ ከሰውነቱ ለጠፋት፡፡የናፈቀውን የእናቱን ጡት እንዳገኘ ህፃን ልጥፍ አለችበት፡፡የተሻለ ምቾት ተሰማት፡፡ከዝናብ ውርጅብኝ የምትሸሸግበት መጠለያ ዋሻ ያገኘች አይነት ስሜት ተሰማት፡፡ እጆቹን በረጠበ ልብሷ ስር ሰቅስቆ በማስገባት ሰውነቷን ላይ አሳረፈና ይዳብሳት ጀመር..፡፡ከዛ ቀስ እያለ ከንፈሩን ከንፋሯ ላይ አሳረፈና በቀስታ ይመጣት ጀመር፡፡አሁን ከውስጧ እየተቀጣጠለ ያለው ሙቀት ወደላይኛው የሰውነት ቆዳ በመድረስ ከላይ የሚያርፋባትን ዝናብ የሚያስከትልባትን ቅዝቃዜ እያተነ የሚያስወግድላት እየመሰላት ነው፡፡ጭልጥ ያለ ምናባዊ ህልም ውስጥ ነው የገባችው፡፡ከንፈራቸው ሳይላቀቅ ዝናቡም ከመቆሙ በፊት እሷ ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡

ስትነቃ ጎጆዋ በጥዋት የደመቀ የፀሀይ ፈንጣቂ አድምቋታል፡፡ሁሉ ነገር ብሩህ ፣ ሁሉ ነገር ዳማቅ ሆኖ ነው እየታየ ያለው፡፡እራሷን ለማንቀሳቀስ ሞከረች፡፡ አሁንም ሰውነቷ እንደተሳሰረ ነው፡፡ወደ ጎን አንገቷን መልሳ ተመለከተች፡፡ ለሊት ጎኗ ተኝቶ የነበረው ጉብል አሁን የለም፡፡አይኖቾን ብታንከራትትም ጎጆው ባዶ ነው፡፡ አንደምንም እራሷን አበረታታ ከተኛችበት ተነሳች፡፡ ዱላ መሰል እንጨት ተደግፋ እንደምንም እግሮቾን እየጎተተች ወደጎጆዋ በራፍ ሄደች፡፡ፊት ለፊቷ ያለው አማዞን ወንዝ እየተገማሸረ ጥሩ አቋም ላይ አንዳለ የማራቶን ራጭ ወደፊት እየገሰገሰ ነው፡፡አካባቢውን የሞሉት ውብና ማራኪ ወፎች ወዲህና ወዲያ አክሮባት እየሰሩ ይዝናናሉ.. አይኖቾን አሩቅ ስታማትር ካርሎስ በ500 ሜትር ርቀት በፓንት ብቻ አማዞን ወንዝ ውስጥ ጠልቆ ገብቶ ዓሳ ላመስገረ ሲዳክር ተመከተችው፡፡ፈገግ አለችና ወደ ውስጥ ተመለሰች፡፡ወደ ሻንጣቸው ተጠጋች ፡፡ውሀ የማያሳገባውን የሻንጣ ዚፕ ከፍታ ውስጥ ያለውን የካርሎስን ማስታወሻ ደብተር ከእነእስኪሪብቶው አወጣች፡፡እዛው መሬት ይዛ ተቀመጠችና ለመፅሀፍ ተዘጋጀች፡፡
ሀሳቧ ለወንድሞ ደብዳቤ ለመፅሀፍ ነው፡፡ለሊት እንዛ በአየሩ ነጎድጓድ ሲረጭ… ከሰማይ ዶፍ ዝናብ ሲወርድ… በውስጧ በተፈጠረባት ፍራቻ ድንገት ብሞትስ? ወንድሜ የሆነ ነገር ሳልለው እንዴት ይሆናል? ብላ አሰበችና በሰላም ለሊቱ ነግቶ ለጥዋት ፀሀይ ከበቃች ለወንድሟ ደብዳቤ ጻፋ እንደምታስቀምጥ ለራሷ ቃል ገባች፡፡ድንገት ብትሞት ካርሎስ ደብዳቤውን ለወንድሞ አንደሚያደርስላት እርግጠኛ ነች፡፡ ደብዳውን መፃፍ ጀመረች፡፡
ወንድሜ-
…የእኔ ትዝታ
ደህና ሁን
….. ቀንና ማታ
ትዝ ይልሀል ይሄን ዘፈን እየደጋገምኩ ስዘፍንልህ? በጣም እኮ ነው የምወድህ...ገና እናታችን ማህፀን ውስጥ ሆነን እንኳን ምርጥ ጎደኛዬ ነበርክ..እና እዛም ሆነን በጣም ነበር የምወድህ...ከተወለድን በኃላም የእናታችንን ግራና ቀኝ ጡት ተካፍለን አይን ለአይን እየተያየን በፍቅር ስንጠባ ሁሉ እወድህ ነበር...ወላጆቻችን ሞተው ቤታችን ሁሉ በለቀስተኞች ተሞልቶ ዋይ ዋይ በሚባልበት በዛን ወቅት እናትና አባቱን አጥቶ ወንድሜ እንዴት ይቋቋመዋል?ብዬ አጨነቅ ነበር...ግን እኮ የሞቱት የእኔም ወላጆች ነበሩ፤የተጎዳሁት እኔም ነኝ...ግን ደግሞ ከእኔ በላይ አንተ ታሳዝነኝ ነበር።ጎዳና ተጥለን ስንኖርም የእኔ ረሀብ ሳይሆን ያንተ ሆድ መንጓጓት ነበር የሚያሳምመኝ።ብቻ ገና ከፅንሰታችን ጀምሮ እስከዚህች ሰዓት ድረስ አንተ ብቸኛ ወንድሜ ነህ...አንተ ብቸኛ የልብ ጓደኛዬ ነህ...አንተ ብቸኛ ዘመዴና የልቤም የነፍሴም ሰው ነህ።

ከመጽሐፍት መንደር💠

23 Nov, 16:26


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-26
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ፔሩ/ኢኪዬቶስ
ጥዋት ምስራቅ እና ናኦል ከእንቅልፋቸው አርፍደው ቢነቁም እርስ በርስ ለመተያየት ግን ተፋፍረው ነበር፡፡
‹‹ምነው የእኔ ፍቅር አመመሽ እንዴ?››ሲል የመጀመሪያውን ዓ.ነገር ተናገረ፡፡
‹‹አይ ደህና ነኝ…ማታ የጠጣውት የሀገሬው መጠጥ መሰለኝ እራሴን አሞኛል፡፡››
‹‹አዎ አንቺ.. እሱ ነው እንዴ …እኔም እኮ ጭፍግግ ብሎኛል››
‹‹መሰለኝ…በል አሁን ልብሳችንን ለባብሰን እታች እንውረድና ቁርስና ብና ነገር እንጠጣበት››
‹‹..እርግጠኛ ነኝ  በቡና ይሻለናል?፡፡››ሁለቱም ተስማሙና ልብሳቸውን ለባብሰው ፊታቸውን ተጣጠቡና ተያይዘው ወደታች ወደሆቴሉ ወረዱ፡፡ ጎን ለጎን ተቀምጠው ቁርስ አዘዙ፡፡ሁለቱም ያስደበራቸው ነገር ምን አንደሆነ ያውቃሉ፡፡ማታ የፈፀሙት ወሲብ ነው፡፡እርግጥ በወቅቱ ሁለቱም ፍፅም ደስታኛ ነበሩ፡፡አሁን እራሷቸውን እስኪያማቸው ድረስ እንዲህ ሀሳብ ላይ የጣላቸው ነገስ እንዴት ነው የምንቀጥለው…?የሚለው ነው፡፡የቀረበላቸውን ቁርስ በልተው ቡናቸውን ጠጥተው ሂሳብ ሲጠይቁ አስተነጋጆ ‹ተከፍሏል› አለቻቸው፡፡ግራ ተጋብተውና ደንግጠው‹‹ማነው የከፈለው ?››ሲሉ በአንድነት ጠየቁ፡፡
‹‹እዛ ጋር ተቀምጦ የነበረው ሰውዬ ነው…ከ5 ደቂቃ በፊት ውጥቶ ሄዶል፡፡ ይሄንን ወረቀት ስጪያቸው ብሎኛል፡፡›› ብላ ብጣሽ ወረቀት አቀበለቻቸው፡፡ናኦል ፈጠን ብሎ ተቀበላትና አንድላይ አነበቡት፡፡
‹‹አሁን ወደ ክፍላችሁ ተመለሱና ሻንጣችሁን ሸክፋችሁ ለጉዞ ዝግጁ ሁኑ፡፡››ይላል፡፡
‹‹ደግሞ ሌላ ጉዞ?››እሱ ነበር ተናጋሪው፡፡
እንደተባሉት ወደ ሆቴላቸው ተመለሱና ሻንጣቸው በፍጥነት ሸከፉ..ወዲያው የሆቴሉ ስልክ ጠራ….ምስራቅ አነሳችው‹‹ወደታች ውረዱ.. ታክሲ ቀሞ ይጠብቃችኋል››የሚል ጎርናና ድምፅ መልዕክቱን ተናገረና ድምፁን አቋረጠው፡፡
ትእዛዙን ተከትለው ..ሻንጣቸውን እንደያዙ ቀጥታ ከሆቴል ሲወጡ ባለታክሲውን አይኑን በጥቁር መነፅር ሸፍኖ በራፍ ከፍቶ ሲጠብቃቸው አገኙ።ያለምንም ንግግር ሻንጣቸውን እየጎተቱ ስሩ ደረሱ።ሻንጣቸውን ተቀበለና ወደመኪናው ኃላ ወስዶ ካሶኒውን ከፈተና ሻንጣዎችን አስገብቶ መልሶ ከደነውና ወደሹፌሩ መቀመጫ ሲሄድ ምስራቅ እና ናኦል ወደውስጥ ገብተው ከኃላ ወንበር ጎን ለጎን ተቀምጠው ነበር።ቀጥታ 25 ደቂቃ በመንዳት ከከተማው ውጭ ነበር የወሰዳቸው።ምን ሊከሰት ነው በሚል ግራ መጋባትና ጉጉት ነገሮችን ሲጠብቁ ቀጥታ ታክሲዎ ቻርተር አውሮፕላን ያለበት ቦታ ደርሶ ነበር ያወረደቻቸው።ከዛ ቆመው እርስ በርስ እየተያዩ ሻንጣቸው ከታክሲዋ ወረደና አውሮፕላኑ ላይ ተጫነላቸው።
ናኦል እና ምስራቅ በተሳፈሩበት አነስተኛ ቻርተር ሄሌኮፍተር ውስጥ ከካፕቴኑ ውጭ ሌላ አንድ ሰው ነው ያለው።ገብተው እንደተቀመጡ መጀመሪያ ሻንጣቸውን እንዳለ ዘርግፎ በውስጡ ያለውን ዕቃ እያብጠረጠረ ተመለከተ። ከዛ በመሳሪያ በመጠቀም መቅረፀ ድምፅ ወይም አቅጣጫ መከታተያ መሳሪያ መያዝ አለመያዛቸውን ፈተሸ።ከዛ በኃላ የሁለቱንም ሞባይል ተቀበለና ያለምንም ማብራሪያ በታክሲ ይዞቸው መጥቶ አሁንም እስኪበሩ ድረስ አታች ቆሞ ይጠብቃቸው ለነበረ የታክሲ ሹፌር በግዴለሽነት ወረወረለት.፡፡አንድን ሲቀልበው ሌላው አምልጦት መሬት ላይ ተፈጠፈጠ.....።ጎንበስ ብሎ አነሳውና ሁለቱንም ኪሱ ከቶ ታክሲው ውስጥ በመገባት መኪናዋን አስነስቶ በመጣበት አቅጣጫ ተመልሶ ሲሄድ በተቀመጡበት ሆነው በገረሜታ ተመለከቱት።
ወዲያው ጎኗቸው ያለው ፈታሻቸው አውሮኘላኑን እንዲያንቀሳቅስ ለካፒቴኑ በእጅ እንቅስቃሴ ምልክት ሰጠው...። ከ3 ደቂቃ በኃላ አውሮኘላኗ አየር ላይ ተሠቀለች።አፍንጫዋን ወደኃላ አዞረችና አረንጎዴ ውቅያኖስ ወደሚመስለው ጥቅጥቅ የአማዞን ደን መክነፍ ጀመረች ።አይናቸውን ዝቅዝቅ ወደታች ሲመለከቱ አማዞን ወንዝ ሰሌሜ ሰሌሜ እየጨፈረ በአማዞን ደን እንብርት ዙሪያ ጥምዝ ሲሰራ የአማዞን ደንን ወገብ ሸብ አድርጎ ለማሰር በእግዜር ከዘንዶ ቆዳ የተሠራ ሰማያዊ ቀበቶ ነው የሚመስለው።
ከሁለት ሰዓት በስጋት የተሞላ ምቾት አልባ በረራ በኃላ አውሮኘላኗ ከፍታዋን መቀነስና አፍንጫዋን ወደታች ደፍታ ለማረፍ መምዘግዘግ ጀመረች። እታች አንድ የተንጣለለ ግቢ ውስጥ ባለአንድ ፎቅ ግዙፍ ህንፃ መኖሩን የታያቸው ለማረፍ መሬት ከተቃረብ ኃላ ነው።
አውሮፕላኖ አርፈ… ሁለቱም ከውስጧ እንዲወጡ ሲደረግ ሜዳው ጠቅላላ እጅግ ዘመናዊ መሳሪያ በታጠቁ አስፈሪ ታጣቂዎች ተሞልቶ ነበር።ናኦል ከመፍራቱ የተነሳ እራሱን ችሎ መቆም አቃተውና ወደምስራቅ ተጠግቶ እጇን ጨምድዷ ያዛት፡፡እሷም የእሱን ያህል አይሁን እንጂ ፈርታለች፡፡ሁኔታዎችም ካሰበቻቸው በላይ አስፈሪና የተወሳሰብ ሆኖባታል። ወዲያው አንድ ታጣቂ ወደእነሱ ቀረበና በተወለካከፈ የእንግሊዘኛ ቃል"ተከተሉኝ"አለና ቀድሞቸው ፊቱን አዙሮ መራመድ ጀመረ...።የተያያዘ እጃቸውን አላቀቁና ተከተሉት  ።
ፊት ለፊት ባለው የህንፃው ትልቅ ባለጣውላ በራፍ እየመራቸው ገባና ወደ ውስጥ ይዘልቃል ብለው ሲጠብቁ ወደጎን በመታጠፍ በደረጃው ወደአንደኛው ፎቅ ይወጣ ጀመር። እርስ በርስ ተያዩና በዝምታ ተግባብተው ተከተሉት። የተወሰነ ኮሪደር ካለፍ በኃላ ግዙፍ አዳራሽ መሳይ ሳሎን ውስጥ ነው ይዞቸው የገባው።
የገብበት ክፍል ሳሎን ነው ብለው ከማሰብ ይልቅ ሙዚዬም ነው ማለት ይቀላል።ግድግዳው ላይ በሰልፍ የተገጠገጡ ግዙፍ ስዕሎች ፣በየቦታው የተቀመጡ ቅርስ መሣይ ውድ እቃዎች፣ በሀውልት ቅርፅ የታነፁ የእንስሳትና የሰው ቅርፆች።ልክ ቱሪስት ሆነው በተጋበዙበት ሙዚዪም ዙሪያ ገባውን እየተዞዟሩ እየጎበኙ ያሉ ነው የሚመስለው።ሁኔታውን በመደመም ከሚመለከቱበት  "የተከበራችሁ ባልና ሚስቶቹ እንግዶቻችን በቀላሉ ወደማይገባበት...ከገብም ወደማይወጡበት የዘላለም ምድራዊ ቤታችሁ ወደሆነው ወደገንት እንኳን በሰላም መጣችሁ።"የሚል ጎርናና ድምፅ ከኃላቸው ሲሰሙ ነው ከተመስጦቸው ነቅተው ወደአሉበት ነባራዊ ሁኔታ እራሳቸውን የሠበሠብት።ሁለቱም በአንድነት ድምፅ ወደሰሙበት አቅጣጫ እኩል ፊታቸውን  አዙረው ተመለከቱ፡፡ ከፊታቸው ያለው ሰውዬ እስከአሁን አካባቢውን ከረገጡ ጀምሮ ካዬቸው ሰዎች የተሻለ የዋህ...ገራገርና ያለቦታው በስህተት የተገኘ የሚመስል ደግ ፊት ያለው ሰው ሆኖ አገኙት ይበልጥ አስገረማቸው።
"ዳግላስ እባላለሁ...ከሀገራችሁ ከኢትዬጰያ ወደእዚህ ያስመጣዎችሁ እኔ ነኝ..ይቅርታ ማለቴ አንተን ያስመጣሁህ እኔ ነኝ ..ባለቤትህ እንኳን በራሷ ፍቃድ የፍቅር ጉዳይ ሆኖባት ነው የመጣችው።"
"ገባን....እንዳልከው ቃልህን አምነን አህጉር አቋርጠን ውቅያኖስ ሰንጥቀን እዚህ ድረስ መጥተናል...አሁን ከእህታችን አገናኘን"ናኦል ነው ጠያቂው።
ዳግላስ ተንከትክቶ ሳቀ....እንደምንም ከሳቁ ወጣና ተጣራ....የተጠራው ልጅ እግር በእጅ አነስተኛ ቦርሳ አንጠልጥሎ እያለከለከ መጥቶ በፍራቻ አንገቱን በመድፍት ስሩ ቆመ "በል ምን ይገትርሀል...ብራስሌቱን አጥልቅላቸው። "ቆፍጣና ትዕዛዝ ሰጠው።

ከመጽሐፍት መንደር💠

22 Nov, 19:40


አኑረን እዳንል ኑረን ምን አፈራን?
ግደለን እዳንል እሳትህን ፈራን
ፀሎቱ ጠፍቶናል በፈለከዉ ምራን

ይሄን ቅኔ ህብረቃሉን
ሰሙን
ወርቁን
መልሱ እስኪ 😁👏👏

ከመጽሐፍት መንደር💠

22 Nov, 08:06


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-25
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ብራዚል/አማዞን ወንዝ አቅራቢያ

ኑሀሚ በሶስተኛው ቀን የሽሽት ጉዞ በህይወትና በሞት መካከል ሆና የመጨረሻዋን ትንፋሿን ለመሳብ ከፍተኛ ጥረት የምታደርግበት ሁኔታ ላይ ወደቀች፡፡ይሄ የሆነው ድንገት ነው፡፡በብራዚል አማዞኑያ ክልል እየጠለቁ ገብተው የአማዞን ደን እየተሸለከለኩ ሰው ያለበት ቦታ ለመድረስ ጥረት ላይ እያሉ ድንገት የሚያምር ቀይና ውብ አበባ አይታ እሱን ለመቀንጠስ እጇን ስትዘረጋ አበባውን ከያዘው የግንድ ቅርንጫፍ ተለጥፎ ያለ እሾክ ነገር ጠቅ አደረጋት፡፡ትንሽ ነው የደም ጠብታ የታየው፡፡ግን ልብላቤው የተለየ የንብ መነደፍ አይነት ነበር፡፡ግን ደግሞ ብዙም ልታካብድ ስላልፈለገች ለጓደኛዋ እንኳን አልነገረችውም ነበር፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ ግን እግሯ መደናቀፍ ስውነቷ መዛል እና በሙቀት መንደድ ጀመረ…ከዛ በግንባሯ ላብ መንቆርቆር ጀመር…
ካርሎስ ድንገት ወደኃላ እየቀረች ስታስቸግረው ዞር ብሎ ሲያያት በጣም ነው የደነገጠው፡፡

‹‹እንዴ ምን ሆነሻል?››

ለመተንፈስ እንኳን እየተቸገረች..‹‹እኔ እንጃ አራሴን ማንቀሳቀስ እያቃተኝ ነው›››

‹‹ታዲያ አትነግሪኝም እንዴ?››አለና ወደእሷ በመጠጋት ደግፎ ለማረፍ ምቹ ወደሆነ ቦታ ወሰዳት እና ምቹ ቅጠል ጎዝጉዞ አስቀመጣት፡፡
ግንባሯን በእጆቸ እየደበሰ ሙቀቷን መለካት ጀመረ…. ‹‹የወባ መከላከያ አልወሰድሽም እንዴ?››
‹‹አረ ወስ..ጄ..ለሁ››በተቆራረጠ ትንፋሽ መለሰችለት፡፡

ግራ ገባው…‹‹.እስቲ ግንዱን ደገፍ በይ…››አላት፡፡
ደገፍ እንድትል ሲረዳት የቀኝ እጇን የመሀል እጣት ተመለከተ ….ለብቻው ተነርቶ አብጧል፡፡‹‹እንዴ እጣትሽን ምን ሆነሽ ነው?››
እይኗን ወደእጣቷ ወረወረችና አየችው…ደነገጠች‹‹ወይኔ ከደቂቃዎች በፊት እሾክ ወግቶኝ ነበር፤ቀላል አድርጌ ነበር የወሰድኩት፡፡››
አስከአሁን ከደነገጠው በላይ ደነገጠ፡፡ትከሻው ላይ ያለውን ጠመንጃ አወረደና አቀባብሎ ስሯ አስቀምጦ በእጇ አስያዛትና ‹‹የሆነ ነገር ካየሽ ተኩሺ… ስለምሰማ በአስቸኮይ እመጣለሁ…መድሀኒት መፈለግ አለብኝ …. ከዚህ እንዳትንቀሻቀሺ ››አለና፡፡ ጓዙን ጠቅላላ ከጎኗ አስቀምጦ ሽጉጡንና እና ጩቤውን ይዞ ሄደ….ከ15 ደቂቃ አታካች እና አድካሚ ፍለጋ በኃላ ነው የሚፈልገውን ቅጠል ያገኘው፡፡በጥንቃቄ ቆረጠውና ተመልሶ ሲመጣ እሷ ሙሉ በሙሉ እራሷን ስታ ተዘርራ ነበር፡፡
ቶሎ አለና ትንፋሿን አዳመጠ፤በትንሹ ቲር ቲር እያለች በውስጦ ትንፈራገጣለች፡፡ እጇን አነሳና ጉልበቱ ላይ አስተካከሎ አስቀመጣት፡፡ወገቡ ላይ የሻጠውን ጩቤ ከጎኑ አወጣና የተመረዘውን የመሀል እጣቷን ሸረከተው፤ጥቁር ደም ከውስጡ መንፎልፎል ጀመረ፡፡ይበቃል በሚለው መጠን ካፈሰሰ በኃላ የጨቀጨቀውን ቅጠል እየጨመቀ ፈሳሹን ወደውስጥ ያንጠባጥብ ጀመረ፡፡ከዛ ሙሉ የእጇን መዳፍ ውጩንም ውስጥንም በቅጠሉ ጠቀለለውና ከስር የለበሰውን ካኔቴራ አውልቆ በመቀዳደድ ልክ እንደፋሻ ጠቀለለውና በቀስታ አስተካክሎ ሰውነቷ ላይ አስቀመጠው፡፡ እሷን ፎጣ ነገር አልብሶት ወደቦታዋ መልሶ አስተኛትና ውጤቱን መጠበቅ ጀመረ…በጣም ተጨንቋል፡፡ይህቺን ልጅ በዚህ ደን ውስጥ ካጣት ከዛ በኃላ ያለው ህይወት እንዴት ሊቀጥል እንደሚችልም ምንም አያውቅም…ከሳምንት በፊት ያወቃት ሳይሆን እድሜ ልክ በልቡም በነፍስም የነበረች ሴት እንደሆነች ነው እያሰበ ያለው፡፡አሁን እጁ ላይ ከሞተችበት ልቡም ሆነች ነፍሱ ከዚህ በፊት ቦዳ ከሆነችው በላይ በጥልቀት ባዶ ትሆናለች፡፡ለመኖር ወኔም ፍላጎትም አይኖረውም፡፡በዚህ እርግጠኛ ስለሆነ ውስጡን በረደው፡፡
ስለእሷ እያሰበ የእሷን መንቃት እየተጠባበቀ ሳለ የሆነ ጆሮው ላይ ሿሿሿ የሚል ድምጽ ሰማ…ይሄ ድምፅ የወንዝ መስገምገም ድምፅ እንደሆነ ያውቃል፡፡ጆሮውን በደንብ ቀስሮና ስሜቱን ሰብስቦ እርግጠኛ ለመሆን አዳመጠ፤ትክክል ነው….ተነሳ ቆመ፡፡ የእሷን ቦርሳም ሆነ እሱ ይዞ የነበረውን ሻንጣ ውስጥ ከተተ፡፡ ሽጉጡንም ከተተና በተከሻው አዘለው…ከዛ ጎንበስ አለና እሷን ልክ እንደተወዳጅ ልጁ በጥንቃቄ ከስር ሰቅስቆ ያዛትና አቅፎ ወደላይ አነሳት፡፡የገመተውን ያህል አልከበደችውም….‹‹ድሮስ በፍቅር የተሸከሙት ሸክም የክብደቱን ያህል መች ይፈተናል?››አለና በውስጡ አሰበ ፡፡እሷን ተሸክሞ ከሀረጋ ሀረጎች እና ከጥሻዎች ጋር  እየታገለ  ለ15  ደቂቃ  ወንዙ  ሿሿሿታ  ወደሚሰማበት  አቅጣጫ  ይዞት  ተጎዛ፡፡ የሚንፎለፎለው ወንዝ የአይኖቹ እይታ ውስጥ ሲገብ ውስጡ በእርካታ ሀሴት አደረጋች፡፡ወደወንዙ ዳርቻ ተጠጋና ምቹ ያለውን ቦታ መርጦ ቀስ ብሎ ተንበረከከና አስቀመጣት ››ወዲያው ደህና ደህና ችካል መሰል እንጨቶችን መርጦ ጉድጎድ በመቆፈር አስተካክሎ ተከላቸው፡፡በአግዳሚ ማገር አራቱንም ኮርነር አገናኛና አርብራብ ሰራላቸው…እዛ እርብራብ ላይ ምቹና ለስላሳ ቅጠል ለምልሞ ጎዘጎዘበት፡፡በመቀጠል ረጃጅም ቋሚዎቹን ቆራረጠና አራት ቦታ ተክሎ ልክ እንደጎጆ ቤት ከላይ ጫፋቸውን አንድ ላይ ሰበሰባና በሀረግ አሰራቸው፡፡ከዛ እንደክብ ዙሪያውን እያሽከረከረ አሰረና አጠናካረው.፡፡ከዛ ኮባ መሳይ ሰፊ ቅጠሎችን በመመልመል አለበሰውና በግማሽ ቀን ውስጥ የሚያምር ጊዜያው ጎጆ ሰራ፡፡ከዛ ኑሀሚን ከመሬት ላይ አንስቶ በጥንቃቄ ወደጎጆው አስገባትና ያዘጋጀላት ርብራብ ላይ አስተኛት፡፡ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን ኑሀሚ ከገባችበት ሰመመን አልነቃችም..ጥሩ ነገር ግን ሙቀቷ በመጠኑ ቀንሶ  አተነፋፋሶም እየተስተካከለ መጥቶ የሰላም እንቅልፍ የተኛች መስላለች፡፡ስለዚህ ሰውነቷ ለመድሀኒቱ ለመልስ እየሰጠና በሰውነቷ የገባው መርዝ እየተዳከመ እና እየተወገደ እንደሆነ ስላመነ ተረጋግቷል፡፡
ልብሱን አወላልቆ ወደወንዙ ውስጥ ገባና እየዋኘ በዛውም አራት የሚሆኑ አሳዎችን አሰገረና ከወንዙ ወጥቶ ልብሱን በመለባበስ ወደሰራት ጎጆ ተመልሶ እንጨት እርስ በርስ በማፋተግ እሳት አቀጣጥሎ ዓሳውን መጥበስ ጀመረ፡፡ልክ የመጀመሪያውን ዓሳ አብስሎ ጨርሶ ሁለተኛውን እያዘጋጀ ሳለ ኑሀሚ አይኖቾን ገለጠች፡፡ብዣ እንዳለባት ነው፡፡ሞት ጫፍ ላይ ደርሶ መመለስ አይነት ስሜት እየተሰማት ነው፡፡ዙሪያውን ስትቃኝ ጥቅጥቅ የአማዞን ድን ሳይሆን አዲስ የተሰራ የገጠር ጎጆ ቤት ነው የሚታያት፡፡አይኖቾን ስታሽከከረክር በጎጆዋ በራፍ አሻግራ ስታይ ሰማያዊ የጠራ መልክ ያለው ወራጅ ወንዝ ይታያታል..ከወንዙ ማዶ ግን መልሶ በግዙፍ ዕድሜ ጠገብ ዛፎች የተዋቀረ ጥቅጥቅ ደን ነው የምታያት…እይታዋን ወዳለችበት ስታጠብ ጭስ ነገር አየች…ቀስቀስ ስትል ድምፅ ስለሰማ የያዘውን ነገር ጣጣለና ተፈናጥሮ ተነስቶ ስሯ ቆመ….‹‹ነቃሽ…?እንዴት ነሽ ..?አሁን ምን ይሰማሻል?››በጥያቄ አጣደፋት፡፡
‹‹በጣም ደህና ነኝ..ፍፁም ሰላም ነው እየተሰማኝ ያለው…እንዴት እዚህ መጣን …?የሆነ ዛፍ ስራ አልነበርኩ..?ወንዙ ከየት መጣ?፡፡››
‹‹ትክክል ነሽ…በአካባቢው ወንዝ እንዳለ ሳውቅ ወደእዚህ ይዤሽ መጣሁና ይህቺን ጎጆ ሰራሁ..አሁን ቆንጆ የዓሳ ጥብስ ሰራቼለው፡፡እሱን ስትበይ ደግሞ ጠንካራ ትሆኚያለሽ››
‹‹ይዤሽ መጣሁ ስትል..እንዴት አድርገህ…?መቼስ በእግሬ መንቀሳቀስ አልችልም ነበር..አይደል እንዴ?››
‹‹ያው አቀፍኩሽና አመጣሁሽ..እሩቅ እኮ አይደለም..አንድ ሶስት ኪሎ ሜትር ቢርቅ ነው፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

19 Nov, 19:31


የውበትሽ ምስጢሩ 😉

❤‍🔥ውበትሽ አይደለም እኔን የማረከኝ
ሁሉን ሴት አስትቶ አንቺን ያስወደደኝ 💘
ፀባይሽ አይደለም ከሌሎች የላቀው
እጅግ ብዙ እንስቶች ውብ ፀባይ አላቸው
ቁመትሽ እንዳልል አውቃለሁ መለሎ💓
ቀልብን የሚሰርቅ ልብንም አማሎ
አይንሽን እንዳልል ጥርስሽን እንዳልል💕
ም/ትም አይሆንም ብዙ እንስቶች በሱም ተክነዋል
ብቻ ምን አለፋሽ የመዋደዳችን💞 ምስጢሩ የሆነው💖
ግራ ጎኔ ሆነሽ በመፈጠርሽ ነው።💓💔

ከመጽሐፍት መንደር💠

19 Nov, 19:06


ማሪኝ ብዬሻለሁ :
ቆዳዬ ተገፎ ይሁንልሽ ጫማ
ስጋዬም ይደገም ለአንቺ ከተስማማ
አጥንቴን ይብረደው እራቁቴን ልሂድ
ከአንቺ የበለጠ አላገኝም ዘመድ
ጥፋተኛው ገላ :
አልወድሽም ያልኩት ውሸቴ ውሸቴ
እምቢ አለኝ ያላንቺ አፍ አወጣ ቤቴ
ያልሆንኩትን ብሏል ይቀጣ ምላሴ
ገና ወድሻለሁ ይጠየቅ ትራሴ
ዝም :
ቢያዳልጠኝ ስሜት እግሬን ለደቂቃ
ዛሬ አፍራለች ነፍሴ ከፀፀት ማጥ ወድቃ
አንቺ አልወጣሽ ከአልጋ አላየሽ ሌላ ሰው
ይብላኝ ማለት እንጂ እንደኔ ላለ ሰው
ልቤን እምቢ አለው :
ፀፀት ታቅፌ ብቻዬን በናፍቆት ልቤ ሲጉላላ
በረዶ ቤቴን አየሁት ጓዳው ከአሁኑ ሲላላ
ልቤን እምቢ አለው ብዙ ነው ለውጤ
ንፁህ ሰው ገፋህ እያለኝ ውስጤ


የማን ዘፈን ነበር 🤔🤔🤔

ከመጽሐፍት መንደር💠

19 Nov, 06:08


አስኮ ባስ መያዣ ጋር ነው ማውቃቸው..ከዛች ቦታቸው አይጠፉም።ረጅም ናቸው።ሙሉ ሱፍ ያዘወትራሉ።ጫማቸው ሁሌ ንፁህ ነው። ቁመታቸው ዘለግ ያለ ሽበታም አዛውንት ናቸው።እጃቸውን ወደኋላ አጣምረው ለባስ የተሰለፉ ሰልፈኞችን እየቃኙ ሲንጎማለሉ ላየ የአንበሳ ባስ አመራር ወይ ተራ አስከባሪ ይመስላሉ።እሳቸው ግን አይደሉም...
ብዙ አያወሩም፤ ብዙ አይስቁም ብቻ ግን አንዳንዴ ተቃቅፈው የቆሙ ወይ አፍ ለአፍ ገጥመው የሚያወሩ ፍቅረኛሞችን ሰልፉ መሀል ሲያዩ አፋቸውን እንደገጠሙ ይፈግጋሉ፣በነጭ ፂም የተወረሰ ጉንጫቸው ሲሸበሸብ ደሞ አንዳች ሞገስ ያላብሳቸውም።ለምን አይስቁም?መች ይሆን ጥርሳቸውን የማየው??እያልኩ አስባለሁ። እሳቸው ግን ወይ ፍንክች ....
ዛሬ ወደቤት ለመግባት ስራ አምሽቼ በመጨረሻው ባስ ለመሄድ ተሰልፌ ሳለሁ ከኋላዬ መጥተው ቆሙ።አላወሩኝም። እንደለመዱት እጃቸውን አጣምረው አንገታቸውን አቀርቅረው ብቻቸውን እያልጎመጎሙ ሳለ
ወደኛ ሰፈር ኖት እንዴ አባባ??አልኳቸው ፍርሀት እያኮላተፈኝ
አዎ ለማለት በዝምታ አንገታቸውን ነቅንቀውልኝ ሲያበቁ
"ሰራተኛ ነህ" አሉኝ
ድምፃቸውን ለመጀመርያ ጊዜ በመስማቴ ደስ ብሎኝ አዎ
አልኳቸው ሲያወሩ ይኮላተፋሉ
ግን አባባ ከዚህ ሁሌ አይጠፉም ስመጣ አላጣዎትም እና...
ስራዬ ነዋ የኔ ልጅ።(አሉ እየተንተባተቡ᎐᎐ ጨለምለም ስላለ በደንብ አይታዩኝም
እዚህ ምንድነው የሚሰሩት አልኳቸው
ስራዬ እሷ ናት ልጄ..በህይወቴ ሌላ ስራ ሰርቼ አላውቅም አንድ የማውቃት የኔ ስራ እሷ ብቻ ናት አሉ
ማናት አባባ???
አሁን ታያታለህ አትቸኩል።ድሮ ወጣት ሳለሁ የከንፈር ወዳጅ ነበረቺኝ።ውብ ናት፤የተከበረ ቤተሰብ ልጅ ናት፤ ታድያ አንድ ቀን እኔ ወደሰፈር ለመሄድ አምበሳ ባስ እዚህች ቦታ ስጠብቅ እሷ ደሞ እያወራቺኝ ሳለ ድንገት በሰልፍ ላይ ሳለን ሹፌሩ ወደኋላ ለማለት ሲል እኔና እሷ በቆምንበት ቦታ መጥቶ ወጣብን።እሷ መኪናው ስር ስለነበረች ክፉኛ ተጎዳች እኔ ደሞ....(አባባ አንዳች ነገር አይተው ፀጥ ሲሉ
ከሩቅ የምታበራው መኪና መንገዱ ዳር ወዳለው ቤት ለመግባት ስትጠጋ
መጣች ያቹትና ልጄ... አየካት በመስኮት ውስጥ? ዛሬ ደሞ
አምሮባታል (አሉ ፈገግ ብለው
አልገባኝም አባባ እና እንዴት ተለያያችሁ ምን ተፈጠረ?? (ወደሰፊው ግቢ የምትገባው ነጭ መኪና ላይ አይኔን ተክዬ
ያ መኪና እሷን ክፉኛ ስለጎዳት አካል ጉዳተኛ አደረጋት።በሰአቱ ቤተሰቦቿ ከኔጋር ሆና መጎዳቷን ሲሰሙ ፈፅሞ እንዳንገናኝ ወሰኑብን።የኔ ፍቅር እግሯን አንደበቷን በህይወት አንዲት ክስተት ስታጣ እኔ ደሞ ህይወቴን አጣሁ።ይኸው እስካሁን ከወንድሞቿ ጋ ስትወጣ ስትገባ አያታለሁ እሷም ባታወራ እንኳ እጇን መስታወቱ ላይ እየለጠፈች ሰላም ትለኛለች።በቃ የኔ አለም እሱ ነው የኔ ደስታ መዳፏን ማየት ነው።(ብለው ከንፈራቸውን ገልጠው ለመጀመርያ ጊዜ ሲስቁ አየኋቸው።ጥርስ የሚባል የላቸውም ቀይ ድዳቸውን አየሁትና ደንግጩ ሳፈጥ
ያኔ እሷ አካሏን ስታጣ እኔ ሙሉ ጥርሴ ረገፈ።የሚያሳዝነው ግን እሱ ሳይሆን አብሮ ሳቄም መሠረቁ ነው።''እኔም
ላልስቅ ጥርሴም ላይበቅል ተለያየን አሁን ብቻዬ
አንሾካሹካለሁ አንተ እንዳስደነገጠህ ነገሩ ለኔም ክፉኛ
የከበደ ነበር።ታድያ የቱን አዋቂ የቱን አላዋቂ እንኮንናለን?? አየህ በህይወት አንዲት ክስተት የሠውን አደለም የአለምን ሁኔታ የመገለባበጥ አቅም አላት።የሚቆጭ ትላንት እንዳይኖርህ በማስተዋል ኑር አንድ ማትደገም ህይወት ላይ ብዙ ስህተት አትስራ ተጠንቅቆ መራመድ ከእንቅፋት ያድናል።በል ደህና እደር
ትኬት ያዝ አንተ!!!ተራ አስከባሪ ሲያንባርቅ እየተደናበርኩ ወደ ባሱ ገባሁ።አባባ የፍቅር ሰው
ትንሽ ዝም ብለው ካዩኝ በኋላ ጀርባቸውን ሰጥተውኝ ሄዱ።

✍️ቻቻ

ከመጽሐፍት መንደር💠

18 Nov, 17:13


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-24
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ከተማው ውስጥ ሲዞዞሩና በከፊል የተጨነቀ በከፊል ደግሞ በከተማዋ ውበት ልብ የተሰረቀ ጥንድ ባልና ሚስቶችን ገፀ ባህሪ እየተጫወቱ አመሹ ፡፡ምሽት ላይ አዛው አልጋ የያዙበት ሆቴል መጠጥ እየቀማመሱና እየተጫወቱ ሰዓቱን ከገፉት በኃላ አራት ሰዓት አካባቢ ከተወሰነ ሞቅታ ጋር ወደ መኝታቸው ተመለሱ፡፡እንደገቡ እሷ የለበሰችውን ልብስ አውልቃ ስስ ቢጃማ ቀሚሶን ለበሰችና ተበትኖ የዋለውን ፀጉሯን አንድ ላይ አሲዛ በጨርቅ በማሰር አንሶላውን ገልጣ ከውስጥ ገባች..እሱም በተመሳሳይ የለበሰውን ልብስ አወላለቀና ወደሻንጣው ሄደ፡፡ ሀሳብ እሷ እንዳደረገችው ቢጃማ ፈልጎ ሊለብስ ነበር…ግን በህይወቱ ቢጃማ ለብሶ የመተኛት ልምድ ስለሌለው ቀጥታ ሰውነቱ ላይ በቀረው ፓንት ብቻ ወደአልጋው ሄደ፡፡ ብርድልብሱንና አንሶላውን ገለጠና ከስር ገባ …ወደእሱ ዞረች…ሰውነታቸው ሲነካካ የሁለቱም የሙቀት መጠን ወደላይ ተስፈነጠረ፡፡እሱ ክንዶቹን በአንገቷ ስር ሰቅስቆ አስገባና አቀፋት ..አንገቷን ከትራሱ ላይ ቀና አደረገችና ደረቱ ላይ ተኛች፡፡በአንገቷ ስር የተሻገረው እጁ ተመለሰና በከፊል የተጋለጠው ቀኝ ጡቷ ላይ አረፈ…፡፡ጭንቅላቷ ድረስ ነዘራት፡፡
አካሄዱ ስላላማራት በጥበብ አእምሮውን በመበታተን ልታስቆመው አሰበች..‹‹የእኔ ፍቅር ኑሀሚ እዚህ ከተማ ያለች ይመስልህል?፡፡››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እዚህ ያለች ይመስለኛል››በእርግጠኝነት መለሰላት፡፡
‹‹ታዲያ ለምን ዛሬውኑ ሳያገናኙን?››
‹‹ያው ምንም ቢሆን እነሱ ባሉት መሰረት ብቻችንን እንደመጣን እስኪያረጋግጡ መሰለኝ››
‹‹እንዴ ምን ነካሽ? በእህታችን ነፍስ እንዴት ቁማር መጫወት እንችላለን…?የአካባቢው መንግስት አቅም ቢኖረው እኮ እስከአሁን ያገኛትና ወደሀገሯ ይመልሳት ነበር፡፡››
‹‹እሱስ እወነትህን ነው..ይሄንን ምናውቀው ግን እኛ ነን..እነሱ የሆነ ነገር ያደርጋሉ ብለው ቢጠረጥሩ ስህተት አልሰሩም፡፡››
‹‹ይሁን እንዳልሽ፡፡እርግጠኛ ነኝ ነገ ብቻችንን መሆናችንን በራሳቸው መንገድ ያረጋግጡና ከእህቴ ያገናኙኛል የሚል እምነት አለኝ››
‹‹አንተ ..››አለችና በድንጋጤ ከደረቱ ላይ ተነሳታ ንግግሯን አራዘመች‹‹ሚስቴ አብራኝ ትመጣለች ብልህ ነግረሀቸዋል እንዴ?››ያላሰበውን ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

እሷ ድራማውን በደንብ አድርጋ እየተጫወተችና እነሱ ጋር እንዲደርስላት የምትፈልገውን መልእክት እንዲናግር ሂሳቡን በመስራት ነበር ጥያቄዎችን የምታቀርብለት..እሱ ግን የእሷ ከእሱ ተከትሎ ፔሩ ድረስ መምጣት ከሰዎቹ ጋር ባደረገው በእስከአሁኑ ንግግራቸውም ሆነ ስምምነታቸው ላይ ስላልነበረ..ይሄ በራሱ እንቅፋት እንዳይሆንባቸው ስለፈራ ደነገጠ፡፡
‹‹አንቺ እስከአሁን ማሳወቅ ነበረብኝ…ምን አይነት የማረባ ሰው ነኝ››አለና ከተኛበት በመነሳት አልጋውን ለቆ ወረደ…
‹‹ወደየት ልትሄድ ነው?››

‹‹ነገ ሲመጡ አይተውሽ ሌላ አለመግባባት ውስጥ ከምንገባ አሁኑኑ በኢሜል ላሳውቃቸው፡፡››
ከተኛችበት ሆና ‹‹ጥሩ አስበሀል ማሬ… ፃፈላቸው፡፡››ስትል ፍቃድ ሰጠችው፡፡
እስከአሁን ሳልነግራችሁ የዘነጋሁት አንድ ጉዳይ አለ፡፡ይቅርታ..ባለቤቴ ወደማላውቀው ሀገር ብቻዬን ልትልከኝ ፍቃደኛ ስላልሆነች አብራኝ ተከትላኝ መጥታለች..ቀድሜ ላሳውቃችሁ ብዬ ነው፡፡››
ብሎ ፃፈና ላከው፡፡እና ሞባይሉን ይዞ ወደአልጋው ተመልሶ በመሄድ ከውስጥ ገብቷ ተኛና ምስራቅን መልሶ አቀፎት ለላከው መልዕክት መልስ ይጠብቅ ጀመር፡፡ወዲያው የኢሜሉን መልእክት መልስ መጣለት፡፡
ቀድመህ ልታሳውቀን ይገባ ነበር…ደግመህ ከተስማማንበት ውጭ የሆነ አንዲት ቅንጣት ነገር ብታደርግ እህትህን ማግኘቱን እርሳው፡፡ለጊዜው የሚስትህን መምጣት ተቀብለነዋል፡፡ግን ደግሞ ለአንተ የነገርናቸውን ማስጠንቀቂያዎች እሷም እንድታከብር የማድረግ ኃላፊነቱ ያንተው ነው፡፡
ይላል ፡፡ምስራቅንም አስነበባትና ስልኩን አስቀምጦ መብራቱን አጠፋና አቅፎት ተኛ… ወደጆሮዋ ጠጋ ብሎ በሹክሹክታ‹‹ደህና እደሪ››አላት
‹‹እንቅልፍህ መጣ እንዴ?››
‹‹አይ አልመጣም..የሚመጣም አይመስለኝም..እኚ ሰዎች እስከአሁን ሙሉ በሙሉ ያመኑን አይመስለኝም፣ማለቴ ባልና ሚስት መሆናችንን›› አለችው፡፡
ጆሮዋ ላይ ተለጥፎ‹‹አረ ያምኑናል…እንዲህ እየሆን እንዴት ላያምኑን ይችላሉ? ››
‹‹ባልና ሚስቶች እንዲህ ብቻ አይደለም የሚሆኑት፡፡ይህንን አታውቅም እንዴ? ››
ምን ለማለት እደፈለገች ቢገባውም ያልገባው ለመምሰል ሞከረ ‹‹እንደምታውቂው ከዚህ በፊት አግብቼ አላውቅም… እንዴት ላውቅ እችላለሁ?››
‹‹ለማወቅ እኮ ማግባት አይጠበቅብህም››አለችው በሹክሹክታ
‹‹ታዲያ ምን ይሻለናል እያልሽ ነው?››
‹‹ኑሀሚን አደጋ ላይ የሚጥል ምንም አይነት ስህተት መስራት የለብንም፡፡ አሁን እንተሻሻለን››
..ቀስ ብዬ ልብሴን አወልቅና ወደወለሉ ወረውራለው፡፡ አንትም ፓንትህን ታወልቃለህ ….እኔ ጭን መካከል ትገባለህ..ልክ ወሲብ እንደሚያረግን ባልና ሚስት በንቅናቄና በድምፅ ማስመሰል እንቀጥላለን..ግን በምንም አይነት ሁኔታ እትንህን ጭኔ ውስጥ የእውነት ለመክተት እንዳትሞክር››
‹‹ተንሸራቶ ከገባብኝስ?››
‹‹ወደሀገራችን ስንመለስ ግንባርህን በሽጉጥ አፈርሰውና ባርቆብኝ ነው ብዬ ቃል እሰጣለሁ፡፡››
‹‹ተስማምቼለሁ›› አለና ሙሉ በሙሉ ወደእሷ በመዞር ከሰውነቱ አጣብቆ ያሻት ጀመረ..እሷም ቀስ በቀስ እያደገ እና እየጨመረ በሚሄድ በተቆራረጠ ድምፅ በማጀብ እጆቾን በእርቃን ሰውነቱ ላይ ታመላለስ ጀመር…ድምፃቸው ምን አልባት እየቀረፃቸው ያለው መቅራጫ በጭለማ ምስል ማስቀረት ባይችል እንኳን ወሲብ ላይ መሆናቸውን የሚያበስረውን ድምጽ በትክክል ማስቀረት ስላለበት በደንብ ነበር የተወኑት ፡፡ከ10 ደቂቃ መተሻሸት በኃላ እሷ ቀድማ ከእቅፉ ወጣችና የለበሰችውን ቢጃማ ሆነ ፓንት አወቀለቀችና ወለል ላይ ወረወችው..እሱም ፓንቱን አወለቀና ተመሳሳዩን አደረገ ..ሙሉ በሙሉ እርቃናችውን እርስ በርስ ተጣበቁ ..እሱ ግን የተሰጠውን ትዕዛዝ ማክበር አልቻለም፡፡ከ5 ደቂቃ መፋተግ በኃላ የእሷም ብልት በፈሳሽ መረጣጠቡን ተከትሎ ሙከራው ከሸፈበትና ብልቱ አዳልጦት ከማንነቷ ጋር ሙሉ በሙሉ ተዋሀዳት..ሁለቱም የሆነውን ያወቁት የመጨራሻ ጡዘት ላይ ደርሰው በእርካታ ወደ ስሜታቸው ስክነት ከተመለሱ በኃላ ነው፡፡ምንም አላላች፡፡ከተወሰነ ደቂቃዎች እረፍት በኃላ ሰውነቷ ላይ የነበረውን ብርድልብስ ገፋ አስወገደችና ከአልጋው ወርዳ ወደግድግዳው በመሄድ መብራቱን አበራችው..ይሄንን ሆነ ብላ ነው ያደረገችው..ናኦል ዝርግትግት ብሎ እርቃኑን አልጋው ላይ ተኝቷል ..ቀጥታ ወደሻወር ቤት ሄደች፡፡
ሻወር ቤት ገባችና ውሀውን ከፈተች፡፡ መሀከል አናቷን ማስመታት ጀመረች…አሁን ያደረገችው ነገር ምን እንደሚያመጣባት ምንም እርግጠኛ መሆን አልቻለችም…እሷ በህይወቷ ከመቶ በላይ የማትፈልጋቸውን ወሲባዊ ተራክቦ ከብዙ የማትፈልጋቸው ሰዎች ጋር አድርጋ ታውቃለች፡›ቀድሞውንም አእምሮዋን አሳምና ስለምትከውነው ምንም አይነት የመንፈስ ቁስለት ሆነ ፀፀት አስከትሎባት አያውቅም ነበር፡፡ይሄ የአሁኑ ግን ከአነዛ በጣም የተለየ ነው፡፡ በመጀመሪያ ይሄን ልጅ ገና ከ12 ዓመቱ ጀምሮ ታውቃዋለች፡፡ እያንዳንዱን እንቅስቃሴውን ለውጡን እድገቱን በቅርበት ስትከታተል ነው የኖረችው…ልክ እንደታላቅ እህቱ ስትንከባከበው እና ስትጠብቀው ነው

ከመጽሐፍት መንደር💠

17 Nov, 18:22


ከኮንዶም እና ሲጋራ ውጪ ገዝቶኝ አያቅም!!እኔ ደሞ ለምን እንደሆነ ባላውቅም ገና ሲመጣ እራሱ ሰውነቴን ውርር እስኪያደርገኝ ያስጠላኛል።ሌላ ቦታ አይገዛም?? ደሞ በዚ ድህነቱ ላይ ሲጋራ ኮንዶም...ምናለ ቀንስራ ለላጠው እጁ ባዝሊን ቢገዛ??ምናለ ፀጉሩን ቢቆረጥ?? ምናለ ዳቦ ቢገዛበት??ሞጋጋ.....(ብስጭት እያልኩ ጓደኛዬ ላይ እነጫነጫለሁ
እኔ ምለው ረዱ ምን አገባሽ ቆይ ሽቀላሽ አደል እንዴ??


አረ የሱ 10 ብር በአፊንጫዬ ይውጣ!!
እንደው ቆይ ይሄንን ጉድሽን ባየሁልሽ...ሆ..ሰው እንዴት ከመሬት ተነስቶ ሰው ይጠላል...?
ዳኑ በግርምት እያወራችኝ ሰፈራችን የሚመረቀው አዲሱ ስላሴ ቤተክርስትያን በር ላይ ደርሰን
ተሳልመን ገባን።

መቼስ የምእመናኑ ብዛት ጠጠር አያስጥልም።ሰፊው የስላሴ ግቢ ውስጥ ነጭ ኩታ የተነጠፈ እስኪመስል በአሉ ድምቅ ብሎ ታቦታቱ ወጥተው ዝማሬው ጫፍ እስከጫፍ ያስተጋባል።ዳኑ ደሞ በማህበር የሚዘምሩትን ወጣቶች ስለምትወድ ተከታትለን ወደ
ዘማርያኑ እንደቀረብን ነበር ቀና ስል ከዛ ሰይጣን ጨብራራ ሱሰኛ ልጅ ጋ አይን ለአይን የተጋጠምነው...

በስመአብ አረ ይኼንን ሰይጣን ማላይበት የት ልሂድ!!?? (በስጭት ስል ድምፄን መሠሠት የሚያቅተኝ ነገርስ? አንባረቅኳ!!
አረ ቀስ በይ ረዱ..ማነው?ምንድነው??
ያ ሲጋራ የሚገዛው ልጅ ነዋ...እዚህም አየሁት። ደሞ አለማፈሩ...!! (አልኳት ንዴቴ ብሶ ድምፄን ለመቀነስ እየታገልኩ

የታለ በናትሽ አረ አሳዪኝ...
ዳኑ ተሰብስቦ በሚዘምረው ምእመን መሀል በጥፍሯ ቆማ አንገቷን አስግጋ ስታማትር ቆይታ ድንገት ዘጭ ብላ ቆማ ደርቃ ስትቀር ነገሯ አስደንግጦኝ እኔ ፈዝዤ አየኋት..
አንቺ ምን ሆነሻል???ምንድነው
ሚያፈዝሽ??....አትናገሪም እንዴ???አንቺ ዳኑ??

(ትከሻዋን እየነቀነቅኩ ብዙ ከጠሯኋት በኋላ በቆምኩበት ጥላኝ ወደኋላ ዞራ ስትራመድ ተከታትለን ሄዴን አንድ ጥግ ቁጭ አለን
ምንድነው ዳኑ???ይሄ ምን አይነት የተረገመ ሰይጣን ነው???ቆይ አንቺም ታቂዋለሽ ማለት ነው!!??

እረፊ ረዱ ሰይጣን አትበይው!! እረፊ ክፉ አትናገሪ!! በረከት እኮ ነው ረዱዬ በረከ....(ነጠላዋን አይኗ ላይ ሸፍና ተንሰቀሰቀች
ማነው በረከት??ምንድነው???የት ታቂዋለሽ??

በረከት ነዋ.....አንድ ጊዜ ስለሱ ነግሬሽ አልነበር? በረከት ዲያቆኑ...ማለቴ እኔና እሱ...(ዳኑ ፀጥ ስትል ከሆነ አመት በፊት የተፈጠረው ክስተት ትዝ ብሎኝ በቆምኩበት ቁልቁል ተዘረፈጥኩ
አላምንሽም ዳኑ!!!

አዎ ተቀይሯል!!እሱን አይመስልም!!ግን እኔ መልኩ አይጠፋኝም!!ይሄ ሁሉ የኔ ስህተት ነው።ታውቂ የለ ያፈቅረኝ ነበር... ይወደኝ ነበር...የመጀመርያውም የመጨረሻውም እኔ እንደሆንኩ ነበር የሚያምነው።ግን እኔ አልረባም... እስካሁን ከሱጋ የተገናኘንበትን ቀን እረግማታለሁ!!!እሱን አፈቅርሀለው ብዬ የዋሸሁበትን ቀን እረግማታለሁ!!!

ለሊት ከሌላ ወንድ ጋ አድሬ ነጠላውን ተከናንቦ ከማህሌት ሲመጣ የተገናኘንባትን ቀን ረግማታለሁ....ከዛች ቀን
ወዲህ ነው ዲያቆኑ ትሁቱ አገልጋዩ በረከት የጠፋው፤ሱስ የጀመረው፤መስከር የለመደው...ይቅር በለኝ እለዋለሁ
እያልኩ ስፈልገው ኖሬያለሁ ግን ከአባቱ ጋ ሰፈሩን ለቆ እንደወጣ ከሰማሁ ወዲህ...
ዳኑ እንባዋ እንደ ጅረት ከአይኖቿ ሲወርድ የበረከትን ሁኔታ አሰላሰልኩት ከዚህች ቤተክርስትያን በር አይጠፋም።

አንዳንዴ ሲያልፍ ከዛ ሲወጣ አይቼው አውቃለሁ። ብዙ ጊዜ እዛው ቆሞ ሲጃራ ለኩሺልኝ እያለ ላይተር በሚይዝባት እጆቹ ዳኑ ብሎ ክንዱ ላይ የተነቀሰው ትዝ ብሎኝ አንገቴን አቀርቅሬ...
ዳኑዬ ይገባኛል ግን ደሞ አንዴ ሆኗል... በረከት ከቤተመቅደሱ አገልግሎት ይራቅ እንጂ ከክርስቶስ ልጅነት አራቀም።

እኔም በረከትን ማውቀው እዚህ የስላሴ ህንፃ ሲሰራ ለቀንስራ ከመጣ ወዲህ ነው።ታውቂያለሽ....አንዳንዴ ህይወታችን እና ስራችን ይለዋወጥብናል።እግዚአብሔር ተጠቦ አክብሮ አስውቦ የፈጠረውን ታላቅ ቤተመቅደስ በውጪ አፍርሰን በሌላ በኩል ደሞ በገንዘባችን የተዋበ ቤተመቅደስ ሰርተን እልል ብለን እንመርቃለን።

ወደኋላ ግን ስናስበው አፍራሾቹም ሰሪዎቹም እኛው ሆነን እንገኛለን።አየሽ ቤተመቅደስ የሚገነባው ለምእመናን አይን ማረፊያ፤ፎቶ መነሻ፤ሳይሆን የልባቸው ማረፊያ እና መሸሸጊያ እንዲሆናቸው ነው....ምንም ህንፃውን ብናስውበው የኛ ህይወት በእግዚአብሔር አባትነት ካልተዋበ ትርጉም የለውም።''እግዚአብሔር እየፈረሰ ቤቱን የሚያንፅ ሳይሆን.እየታነፀ ቤቱን የሚሰራ ትውልድ ነው ሚፈልገው"

በረከት በዲቁናው ሰወችን ባያንፅ ሰወች የሚታነፁበትን ዛሬ የቆምንበትን መቅደስ ግን በላቡ በጉልበቱ ከማነፅ አልሰነፈም ፈጣሪ ደሞ በጎቹን ጥሎ አይጥልም አንዴ ቃሉን በልቡ የዘራ ከነቆሻሻውም ቢሆን ይመላለሳል እንጂ አይቀርም።ሁሌ አዲስ ቤተክርስትያን እንገንባ እነጂ እኛ ለክርስቶስ ነዘላለም አዳዲስ ህንፃወቹ ነን...አታልቅሺ በቃ በማርያም(እጇን ከአይኗ ላይ አንስቼ ላቅፋት ስል... ሂጄ አገኘዋለሁ ረዱዬ ....(ከተቀመጠችበት ፍንጥር ብላ ተነስታ ወደሚዘምሩ ምእመናንን እየገፋች ስታልፍ ተከተልኳት "በረከት ግን
ቆሞ በነበረበት ቦታ ላይ አልነበረም በረከት
ሄዳል....

✍️
ቻቻ

ከመጽሐፍት መንደር💠

16 Nov, 19:01


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-23
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ብራዚል/ፔሩ
ናኦል እና ምስራቅ የወደቧ ውብ ከተማ ሪዬ ዲጄኔሮ እንደደረሱ ቀጥታ ታክሲ ይዘው ወደ ሆቴል ነው ያመሩት፡፡ለሁለትም እንዲህ አይነት ረጅም የአየር ላይ ጉዞ ሲጓዙ የመጀመሪያቸው ስለሆነ ድካሙ ከልክ ያለፈ ነበር..በተለይ ናኦል ከሀገር ውስጥ በረራዎች በስተቀር ድንበር ሲሻገር እራሱ የመጀመሪያው ገጠመኙ ሰለሆነ ጉዞ እንደህልም ነው የሆነበት ፡፡ሁለቱ ከአየር መንገድ ወጥተው ታክሲ ተሳፍረው ወደሆቴል እየሄዱ እያሉ ከሻንጣዋ የጎን ኪስ አንድ ወረቀት አወጣችና አቀበለችው፡፡
ተቀብሎ እያያት‹‹ምንድነው?፡፡››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹አንብበው፡፡››
የተጣጠፈውን ወረቀት ገለጠና አየው..ከወረቀቱ ጫፍ በግራ በኩል የእሱ ፎቶ ተለጥፎበታል፡፡ በተመሳሳይ መስመር በቀኝ በኩል ደግሞ የራሷ የምስራቅ ፎቶ አለበት፡፡በመደነቅ እንደተሞላ ማንበብ ጀመረ‹‹ሁለቱ ባልና ሚስት እንደሆኑ የሚያወራና ያንንም የሚያረጋግጥ ህጋዊ የጋብቻ ሰርተፍኬት ነው፡፡ባለማመን አይኑን ጨፈን ገለጥ ጨፈን ገለጥ በማድረግ ደጋግሞ አየው፡፡ትክክል ነው፡፡
‹‹ውይ እኔ እኮ በጣም እድለኛ ሰው ነኝ ..መቼ ነው ህልሜ እንዲህ ያሳከሁት?መቼ ነው በአለም ላይ እጅግ የማደንቃትንና የምወዳትን የህልሜን ሴት ያገባሁት….?እስኪ ንገሪኝ መቼ ነው ?››
‹‹ጎረምሳው አረጋጋው..ይሄ ኑሀሚን በመፈለግ ሂደት በጣም አስፈላጊ ጉዳይ ስለሆነ ነው፡፡ይሄንን ተልዕኮችን እስኪጠናቀቅ እኔና አንተ ባልና ሚስት ነን፡፡የተጋባንበትን ቀን በቃልህ ሸምድደው..ሁለት ወር ሆኖናል፡፡ገና ትኩስ ባለትዳሮች ነን፡፡እንኳ…ደግሞ ቀለበትን በትከክለኛ እጣትህ ላይ አጥልቀው›› አለችናን እጇ ላይ ካለው ሁለት ቀለበት መካከል አንድን አቀበለችው፤ ሁለተኛውን እራሷ ጣት ላይ አጠለቀች፡፡ተቀበላትና በሚፍለቀለቅ ፈገግታው ታጅቦ ቀለበቱን አጠለቀው፡፡
‹‹…ይሄው..አሁን ሁሉ ነገር ውብና ፍፅም ትክክል ሆኗል…ግን ይሄንን ሰርተፍኬት እኔ ጋር ቢሆን ምን ይመስልሻል?››
‹‹ግድ የለም ያዘው ..የረሴ ድርሻ አለኝ..››አለችው በፈገግታ፡፡
ከዛ ሆቴል ደርሰው በባልና ሚስት ተመዝግበው አንድ አልጋ ያለው መኝታ ክፍል ያዙ፡፡ከምስራቅ ጋር በጣም በርካታ ቀናቶች ተመሳሳይ ቤት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ክፍሎችና የተለያዩ አልጋዎች ላይ የመተኛት አጋጣሚ ቢኖራቸውም እንዲህ አንድ አልጋ ላይ የመተኛት እድል አጋጥሞት አያውቅም….አሁን ያ እድል እውን ሊሆንለት እንደሆነ ሲያስብ ልቡ በውስጡ መፈንጠዝ ጀመረች፡፡
///
በማግስቱ ከብራዚል ወደፔሩዋ ከተማ ሊማ ተጓዙና ምንም ሳያርፍ ቀጥታ ወደኢኩዬቶስ በረሩ…እንደደረሱ ለኡበሩ ሹፌር የተነገራቸውን ሆቴል ስም ነገሩና ወደዛው ወሰዳቸው፡፡ልክ ከኡበሩ የየራሳውን ሻንጣ ይዘው ወረዱና ወደሆቴል መጓዝ ሲጀምሩ‹‹እንግዲህ ከእስከአሁኑ በላይ በጣም ጠንቃቃ ሁኑ ..ከዚህ ሰዓት ጀምሮ በእርግጠኝነት በእነሱ ሰዎች እይታ ስር ነው ያለነው…ሆቴሉ ውስጥም ሆነ የምንገባበት መኝታ ቤት ውስጥ ካሜራ እንደሚያስቀምጡ እርግጠኛ ነኝ፡፡››አለችው፡፡
‹‹ገባኝ..እጠነቀቃለሁ፡፡››
‹‹ሆቴል ብክ አደረጉና ፅዱ የሆነ ባለአንድ አልጋ መኝታ ቤት ተሰጣቸው፡፡ገብተው ዕቃቸውን አመቻችተው እንዳስቀመጡ..‹‹የእኔ ፍቅር ትንሽ ሞቆኛል ሻወር ልወስድ ነው..አስከዛው ጋደም ብለህ ጠብቀኝ ..››አለችና እዛው እያያት ልብሷን በማወላለቅ እርቃኗን ሰውነቷ ላይ በቀረ ሰማያዊ ፓንት ብቻ ወደ ሻወር ቤት ሄደች፡፡እሱም በፍዘት ሲያያት ቆይቶ ሻወር ቤት ገብታ እስክትሰወርበት እየተመለከታት ነበር.፡፡ሌላ ቀን እዛ ሀገራቸው ምድር ላይ ሆኖ እንደዚህ ፊት ለፊቱ ልብሷን አወላልቃ እንዲህ እርቃኗን ቆማ አይቷት ቢሆን ኖሮ ወይ ተንደርድሮ ሄዶ ይጠመጠምባታል..ወይ ደግሞ እራሱን ስቶ መሬት ይዘረር ነበር፡፡አሁን ግን ከደቂቃዎች በፊት ያስጠነቀቀችውን እያሰበ እራሱን በትልቅ ጥረት ተቆጣጥሮ በትግስት ባለበት መርጋት ቻለ..፡፡
እሷ እየሰራች ያለውን ድራማ ይበልጥ ሊያደምቀው ወሰነና ልክ እሷ እንዳደረገችው ልብሱን አወላለቀ እና በፓንቱ ብቻ ወደሻወር ቤት ሄደና ገርበብ ያለውን በራፍ ገፋ በማድረግ ወደውስጥ ገባ ፡፡አልጠበቀችም ነበርና ስታየው ደነገጠች፡፡ሰውነቷን ስታሽበት የነበረው ሳሙና ከእጇ ተንሸራተተና ወደወለሉ ወደቀባት፡፡
‹‹የእኔ ፍቅር ላሽሽ እኮ ነው የመጣሁት…››አለና ሳሙናውን ጎንበስ ብሎ በማንሳት ሰውነቷን በአራፋው ያዳርስ ጀመር፡፡እሱ ብቻ ሳይሆን እሷም እጆቹ ሰውነቷ ላይ ሲሽከረከሩ ድንዝዝ እያለች ነው፡፡ልትቆጣጠረው የማትችል ስሜት በውስጧ ሲንተከተክና ልቧን ድክምክም ሲያደርጋት እየታወቃት ነው፡፡በዚህ ስሜት ተሸንፋ ዝልፍልፍ ብላ ክንዱ ላይ ከመውደቋ እና ባሳደገችው ልጅ ፊት ከመዋረዷ በፊት የሆነ ነገር ማድረግ እንዳለበት ተሰማት፡፡‹‹የእኔ ፍቅር አሁን ደግሞ ያንተ ተራ ነው..አምጣ ሳሙናውን ልሽህ፡፡››አለችና ከስሩ ሸሸት ብላ ሳሙናውን ከእጁ ተቀበለች፡፡የሻወሩን ውሀ ከፈተችና ሰውነቱን በውሀ እንዲያስመታ ዞር አለችለት፡፡ከፀጉሩ ጀምሮ ሳሙና አስመታና ‹‹በይ እሺኛ ››በማለት ደረቱን ዘርግቶ ወደእሷ ተጠጋ…
‹‹የእኔ ፍቅር ደረትህንማ አንተው በቀላሉ ማሸት ትችላለህ..ጅርባህን ዙርና እሱን ልሽህ››አለችው፡፡እንዳለችው በዝምታ ዞረ፡፡ ጀርባውን ከትከሻው ጀምሮ የፓንቱ ጠርዝ እስኪሚታይበት እስከመቀመጫው ድረስ አሸችውና..‹‹እንካ ጠጋ በልና ፊት ለፊትህን ሰሙና ምታው ..እስከዛ እኔ ልለቃለቅ›› ብላ ሳሙናውን አቀበለችውና የሻወሩን ቧንቧ በመክፈት ሰውነቷን ተለቃለቀች፡፡ድምፅ ሳታወጣ በምልክት ፊቱን ከእሷ እንዲያዞር አዘዘችው…ቅር እያለው ዞረ ፡፡ፓንቷን አወለቀችና መስቀያው ላይ አንጥልላ አንድ ፎጣ ከመስቀያው ላይ አንስታ በእጇ በመያዝ ባዶ መቀመጫዋን እያማታች ከሻወር ቤት ወጣች…እሱም ጥላው እንደወጣች ሲያውቅ ፈጠን አለና ሰውነቱን የሰተለቀለቀውን ሳሙና መለቃለቅ ጀመር…፡፡

ፎጣውን አገልድማ መውጣት እንዳለባት ታውቃለች.፡፡ግን ደግሞ እሷ እንደገመተችው እዚህ ድረስ ያስመጧቸው ሰዎች እዚህ ክፍል ውስጥ ካሜራ ካስቀመጡና እየተከታተሏቸው ከሆነ ከናኦል ጋር ባልና ሚስት እንደሆኑ ይበልጥ ማሳመን አለባት፡፡እርግጥ ለማንም ሰው በተለይ ለአንዲት ሴት በሆነ ቴክኖሎጂ ሰዎች ከርቀት ሆነው እየቀረፃት እንደሆነ እየተጠራጠረች , እርቃኗን በነፃነት የምታሳይ ሴት አትገኝም፡፡እሷ ግን ለዚህ የሰለጠነች ነች፡፡የሆነ የተሰማራችበትን ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ እስከጠቀመ ድረስ ማንኛውንም አይነት የተቀናጀ ተግባሮችን መፈፀም እንዳለባት ታውቃለችም ..ያንን ብዙ ጊዜ ተግባራዊ አድርጋ ውጤት አስመዝግባበታለች…አሁንም እያደረገችው ያለው ተመሳሳይ ነው…የትኛውም ወንድ እንዲህ የሴት እርቃን ገላ እየተመለከተ ጥርት ያለ ሀሳብ ሊያስብ አይችልም፡፡ስሌቷ እንደዛ ነው፡፡
ሰውነቷን በፎጣው አደራረቀቸና ሌላ ቅያሪ ፓንት ከቦርሳዋ አውጥታ እየለበሰች ሳለ ..እሱም ልክ እንደ እሷ በቅጡ ያልተላጨ የተሸፈነ እንትኑን እያማታ መጣ፡፡በቆሪጥ አይታው ወደሻንጣዋ አቀረቀረችና የምትለብሰውን ልብስ መምረጥ ጀመረች፡፡ተጠቅማ ጠረጴዛው ላይ ያስቀመጠችውን ፎጣ እያነሳ…‹‹ማሬ ሰውነቴን በዚህ ላደራርቅ እንዴ?›› ሲል ጠየቃት..፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

15 Nov, 16:42


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-22
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ብራዚልና ኮሎምቢያ ድንበር/አማዞን ደን ውስጥ

‹‹ካርሎስ››

‹‹አቤት››

‹‹ሀገሬ ኢትዬጵያ አባ..ይን ጨምሮ የብዙ ወንዞች ባለቤት ነች..ማለት የፈለኩት ብዙ ወንዞችን አይቼ አውቃለው…እና አማዞን እጅግ ገራሚ ከሆኑ ጥቂጥ ተፈጥሮዎች መካከል አንዱ ሆኖ ነው ያገኘሁት››
‹‹ምኑ ነው ያስገረመሽ?››

‹‹አማዞን አንዴ ወንዝ ይመስላል….አንዴ ደግሞ ሀይቅ ይሆናል ፣አሁን ተሸገርኩት ብለህ ለሳዕታት ከተጓዝክ በኃላ መልሶ ፊትህ ይጋረጣል››
‹‹ጥሩ ታዝበሻል፡፡አማዞን እና ገባር ወንዞቹ በአጠቃላይ ከ25,000 ኪሎ ሜትር በላይ ርዝመት ያላቸው የውስጥ የውሃ መስመሮች መገናኛ ዋና ደም ስር ነው።ይህ ወንዝ ከተለያዩ ሀይቆች ጋር በሚገናኙበት ጊዜ, የወንዙ ጥልቀት 100 ሜትር ይደርሳል፡፡በበጋ ወቅት አማዞን 11 ኪሎ ሜትር ስፋት ሲደርስ 110 ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ቦታን ያካልላል፡፡ዝናብ ሲሆን ደግሞ ስፈቱና ጥልቀቱ በሶስት እጥፍ ይጨምራል፡፡ በዚህ ወቅት የወንዙ ውሃ እስከ 20 ሜትር ከፍ ብሎ ስፋቱ ደግሞ 350 ሺህ ካሬ ኪሎ ሜትር መሬት ይሸፍናል፡፡በአማዞን እና ገባር ወንዞቹ ውስጥ ወደ 3,000 የሚጠጉ የዓሣ ዝርያዎች አሉበት››
ስለአማዞን ጥልቅ የሆነ እውቀት እንዳለው አመነች፡፡ ርእሱን ቀይራ‹‹እንስሳቱ ግን አያሳዝኑም››ስትል ጠየቀችው

‹‹እንዴት ማለት?››

‹‹አንድ አንድን ሲበላ …ጠገብኩ እፎይ ብሎ አረፍ ሲል በሌላው ደግሞ ሲበላ…››

‹‹አዎ ሁሉም እንስሳት ሰውንም ጭምር… ሁለችንም ለመብላትም ለመበላትም ነው የተፈጠርነው…፡፡››
‹‹የሰው ልጅ ደግሞ ይበላል እንጂ ይበላል እንዴ?››

‹‹አዎ … ወይ ቀን ሲጥለው ወይ ደግሞ ቀነ ሲጥል ይበላል፡፡አሁን እኔና አንቺ እዚህ ደን ውስጥ ስንት ቀን ከአውሬ መበላት ተርፈናል…ቀን ቢጥለን መበላታችን ይቀር ነበር…ባለፈው ከጓደኞቼ አንዱ በአናኮንዳ ሲበላ አላየሽም?፡፡
‹‹ያ እኮ ተዲያ ከመቶ ሚሊዬን አንድ የሚያጋጥም ነው፡፡››

‹‹አዎ ..ይሄ የሆነው የሰው ልጅ የሚያስብ እንስሳት በመሆኑ እራሱን ከዚህ አደጋ ለመጠበቅ ምን ማድረግ እንዳለበት እያሰበ እያሰበ መጣና እራሱን ከእንስሳ መኖሪያ እያራቀ መንደርና ከተማ እየሰራ ደህንነቱን ለማስጠበቅ ቻለ..እንደዛም ሆኖ ግን እድሜውን ማርዘም ቻለ እንጂ ሄዶ ሆዶ ከመበላት አይተርፍም….አሁን ስንቶቻችን ነን እርስ በርስ እየተባላላን ያለነው…?እኛ አሁን እዚህ ደን ውስጥ መከራችንን እያየን ያለነው ለምንድነው? በመሰል የሰው ልጆች ላለመበላት አይደል፡፡መበላት ሲባል የግድ ሰጋችንን ፈጭተው መዋጥ የለባቸውም …ከገደሉንና ከህይወት መስመር አንሸራተው ካስወጡን በሉን ማለት ነው፡፡››
‹‹ትክክል ነህ፡፡››

‹‹አዎ ትክክል ነኝ፡፡ ግን ደግሞ ሁሉም እንስሳት እኩል የመብላትና መበላት እጣ አላቸው ማለት አይደለም፡፡የጫካው ህግ የምግብ ስርዓት ልክ እንደፒራሚድ ነው፡፡ከፒራሚዱ የስረኛው ወለል ያሉ መበላት የየእለት ጭንቀታቸውና እጣቸው ነው፡፡የፒራሚዲ ጫፍ ያሉት ደግሞ እነአንበሳ ነብር የመሳሰሉትና ማለቴ ነው..ማደን መያዝና መዘንጠል የየእለት ስራቸውና ተግባራቸው ነው፡፡››
‹‹ተመስገን እኛ የሰው ልጅ እንደዚህ አለመሆናችን፡፡››
ፈገግ ብሎ ሳቀባት፡፡
‹‹ምነው ትክክል አይደለሁም እንዴ?››

አይ እንደውም ይሄንን ፒራሚዱን የምግብ ስርዓት ከእንስሳቱ ኮርጆ የራሱን ማሻሻያ አድርጎበት በጥበብ ነው እየተገበረ ያለው፡፡የአለም 90 ፐርሰንት ሀብት በ10 ፐርሰንት በሚሆኑ ቱጃሮች እጅ ነው ያለው ..ያ ማለት በሰው ልጅ ኪንግደም ውስጥ 10 ፐርሰንቱ የፒራሚዱ ጫፍ ላይ ያሉት ናቸው፡፡እነሱ የ90 ፐርሰንቱን ላብና ወዝ በተለያ ሚስጥራዊና ዘዴ ቅርጥፍ አድርጎ ይሰለቅጡታል፡፡››
አይን አይኗን በስስት እያያት‹‹ስለአንቺ ሳስብ ምን እንደሚገርመኝ ታውቂያለሽ?››አላት

የተወሰነ ጉጉት በሚታይበት የስሜት መነቃቃት‹‹እስኪ ምንድነው ንገረኝ ልስማው ››ስትል መለሰችት
‹‹ያንቺ ነፍስ ያንቺ ብቻ እንዳልሆነች ነው እንድረዳ ያደረግሺኝ..የነፍስሽ ክፍያ የወንድምሽ ንበረት ነው የሚመስለው፡፡አደራ አንቺ ጋር አስቀምጪልኝ ብሎ እንደሰጠሸና ያንን አደራሻን ላለመብላት የመጨረሻውን ጥረት እየጣርሽ እንደሆነ ነው፡፡ያ ነው እንዲህ ብርቱና ጠንካራ እንድትሆኚ ያደረገሽ….››
‹‹ጥሩ ገልፀሀዋል..ግን ይሄ የእኔ ብቻ ችግር አይመስለኝም፡፡የሰው ልጅ ሁሉ ለቤተሰቡ ይብዛም ይነስ እንጂ ተመሳሳይ አይነት እይታ አለው፡፡ማንም ቢሆን ነፍሱ የእሱ ብቻ አይደለም…እሱ ሲያመው የሚያማቸው እሱ ሲደሰት ደስ የሚላቸው ቤተሰቦች ይኖሩታል፡፡ለእነሱ ሲል እራሱን ከአደጋ ይጠብቃል..ለእነሱ ሲል ጠንክሮ ይሰራል፡፡አዎ ጠንካራ የቤተሰብ ትስስር ያለው ሰው ጠንካራ ስብዕና ይኖረዋል፡፡እነሱ በህይወት ጉዞ ትክክለኛውን መስመር መርቶ እንዲጓዝ ብርታትና ጥንካሬ ይሆኑታል፡፡.አብዛኛው ሰው የሚኖርላቸው የሚወዳቸውና የሚወዱት አምስት ወይም አስር ሰዎች ይሩታል፡፡እኔ የእኔ የምለው አንድ ወንድሜ ብቻ ስለሆነ ነው፡፡ያለኝን ፍቅር ጠቅላላ ተሰብስቦና ተከማችቶ አንድ ወንድሜ ላይ ስላረፈ ነው፡፡››
‹‹ገባኝ ..ጥሩ ገልፀሸዋል….ቀናሁበት››

‹‹ግድ የለህም አትቅና፡፡ ፍቅር ከመጠን ሲያልፍ ትንፋሽ ይነሳል…እንዲህ እንደምታስበው ጥሩ ጎን ብቻ አይደለም ያለው፡፡ወንድሜ የ10 ደቂቃ ታላቄ ወይም በሌላ አገላለፅ መንትያዬ ነው፡፡አንድ ማህፀን ውስጥ አንድ አይነት ሰዓት አንድ አይነት ምግብ እየተመገብን ነው የኖርነው…ከተወለድንም በኃላ እንደዛው… ቢሆንም በተለይ ወላጆቻችን ከሞቱ በኃላ ልክ እንደታናሽ ወንድሜ ነው የምቆጣጠረው፡፡የት ገባህ?የት ወጣህ….?በዚህ ግባ በዚህ ውጣ..አንዳንዴ ጭቅጭቄ ለእኔ ለራሴ ይሰለቸኛል..የሚገርመኝ እሱ ግን የእኔን ጭቅጭቅ የሚታገስበት የሚገርም ትእግስት አለው….ዝም ያልኩት ቀን እንደውም ምን ነካት ብሎ ይንቆራጠጣል….፡፡››


አዲስአበባ
///
ናኦል  ከምስራቅ  ጋር እንደተቃጠሩት  በማግስቱ ምሽት  1፡30 ነበር ቦሌ የደረሰው፡፡
‹‹ለሁለት 10 ጉዳይ ሲል ልደውልላት ወይስ ሁለት ሰዓት ይሙላ?›› እያለ ከራሱ ጋር ሲሞገት ከፊት ለፊት ሽክ ያለ አለባበስ ለብሳ በአስፈሪ ግርማ ሞገሶ አንድ መለስተኛ ዘመናዊ ሻንጣ በእጇ በመጎተት እያሽከረከረች ወደእሱ ስትቀርብ ተመለከተ፡፡ፊቱ ሁሉ አንፀባረቀ፡፡
‹‹እሺ..ቀድመህ ነው የደረስከው››አለችው፡፡
‹‹አዎ መቅደምም ነበረብኝ…ግን ሻንጣው ለምን አስፈለገ …?የሚያስፈልጉኝን ነገሮች እንደማልይዝ ጠርጥረሽ ነው አይደል? ዝም ብለሽ ነው የሰጋሽው፡፡››አለ፡፡እሱ ..ሻንጣውን ለእሱ ብላ የሚያስፈልጉትን እቃዎች ይዛበት የመጣች ነው የመሰለው፡፡
‹‹አይ ጎረምሳው ተሳስተሀል..ይሄ ሻንጣ የእኔ ነው፡፡››
‹‹የእኔ ነው ማለት?››
‹‹የእኔ ነዋ …እኔም ተጓዥ ነኝ፡፡ይልቅ ና እንግባ፡፡›› አለችና ከፊቱ ቀደመች፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

15 Nov, 07:18


ይሄን ሰው ከ 4 ዓመታት በፊት ነበር ያወኩት

ዝምተኛ ነገር ነው በዚያ ላይ ዐይናፋር ..ሰፈራቸው እህቴን ፍለጋ ነበር ስሄድ ያየውት ዝምተኛነቱ ታታሪነቱ ኮስታራነቱ ስቦኝ ነበር ..ይባስ ብሎ እሱን የሚያውቁት ሰዎች ሁሉ አውቀው ይመስል አጠገቤ ደግ ደጉን ጨዋነቱን ነበር የሚወራው ..ተመቸኝ ቀርቤ ባወኩት የሚለው ፍላጎቴ ጨመረብኝ ነገር ግን እንዴት??
ትዝ ይለኛል የ covid time ነበር class ተዘግቶ ነበር by the way በሰዐቱ university የ መጀመሪያ ዓመት ተማሪ ነበርኩኝ የዛኔ እሱ ደሞ ሰራተኛ ከዛም ወደ ታሪኩ ስመለስ በቃ በምን ልተዋወቀዉ ሆነ ጭንቀቴ ሁሉ ከዛ ስሙን አውቀው ስለ ነበር fb ላይ search ማድረግ ሆነ ስራዬ ሁሉ ጥረቴም ከንቱ አልቀረም አገኘውት friend request ከራሴ ጋር ታግዬ ልላክ አልላክ ብዬ ላኩኝ የት አባቱ🙄
ከዛግን text yemelak ድፍረት አነበረኝም የተወሰነ ጊዜ ዝም አልኩት fb friend ሆነን ብቻ ቀጠለ ከዛ የሆነ ቀን hii ተባልኩ አቤት ደስታዬ🥹
የመለስኩበት ፍጥነትማ ጌታ ሆይ😁

ከዛ ወሬ ተወራ ተግባባን አይገልፀውም የሚገርመው ውስጤ ፍርሃት ነበረብኝ እንደጠበኩት አይነት ሰው ባይሆንስ የሚል ?? የለመንኩት እግዚአብሔር አላሳፈረኝም ከጠበኩት በላይ ደግ ሰው እግዚአብሔርን የሚፈራ አስተዋይ ብቻ ብዙ ብዙ ሆኖ እርፍፍፍ 😍አለ ተመስገን መድኃኔዓለም 🙏

ከዛ ለተወሰነ ጊዜ like normal ጓደኛሞች ሆነን telegram layem በ ስልክም ማውራታችንን ቀጠልን ስቀርበዉ ይበልጥ ወደድኩት ማንነቱ ገዛኝ የሚገርመው በ txt እያወራን ሰፈራቸው ስሄድ ቀና ብሎ አያየኝም ነበር ...

ብቻ እያልን እያልን አሱም በጊዜው መውደዱን ገለፀልኝ እኔም እንደምወደዉ ነገርኩት በፍቅር አብረን ቀጠልን ብዙ ነገር support ያደርገኛ ማርያምን ጓደኛዬ አማካሪዬ አባቴ ወንድሜ ብቻ ብዙ ነገሬ ነው በ ትምህርቴ እያበረታኝ ወንድነቱ አሸንፎት ሴትነቴን ሳይፈታተነኝ ከጎኔ እንደሆነልኝ ትምህርቴን ጨረስኩኝ family አስተዋወቀኝ አሁን ላይ ሁለታችንም እየሰራን ነው እግዚአብሔር ይመስገን መጨረሻችንን ያሳምርላቹ በሉኝ ለሁላቹም የኔ አይነት ሰው ይስጣቹ❤️🙏

ከመጽሐፍት መንደር💠

12 Nov, 17:23


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-20
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ከምስራቅ ካር ስምምነት ላይ ከደረሱ በኃላ ይገጥመናል ከሉት በላይ በጣም የተወሳሰበው ነገር ነበር የገጠማቸው፡፡በመጀመሪያ የት እንደተወሰዱ ያለማወቃቸው ነበር ከባድ ነገር፡፡ መስታወቱ ደፍን ጥቁር ሆኖ ወደውጭ በማያሳይ መኪና ውስጥ ተከተው…ለአንድ ሰዓት ለበለጠ ጊዜ ሲጓዙ ከቆ በኃላ መኪናዋ ቆመችና ሲወርዱ አምስት የሚሆኑ ባለአምስት ፎቅ ዘመናው ህንፃዎች ያሉበት የእግር ኳስ መጫወቻ ሜዳ፤ የመረብ ኳስ እና የመሳሰሉት ሜዳዎች ያሉበት ዙሪያውን በደን የተሸፈነ እና ቢያንስ 3 ሜትር ሚሆን ከኮንክሪትና ከብሎኬት የተሰራ አጥር ….በአጥሩ ጫፍ ላይ አደገኛ ሽቦ የተጠመጠመበት በጣም አስፈሪ ድባብ የተላበሰ ግዙፍ ስፍራ ነው፡፡በዛ ላይ  .በተወሰነ ሜትር ርቀት በየሰዓቱ በሚቀያየሩ ቆፍጣና የጥበቃ ወታደሮች የሚታዩበት አስፈሪ ግቢ ውስጥ ነው ይዘዋቸው የገቡት፡፡
ይዞቸው ከመጡት መካከል አንድ ወደአንደኛው ፎቅ ይዟቸው ሄደና ወዳአንድ ቢሮ  አስገባቸውና  ምንነቱን ያለወቁት የሆነ ወረቀት አስፈርሞ በማስረከብ ቀሪውን ያዘና አነሱንም ልክ እንደወረቀቱ እዛው ጥሎ ወጥቶ ሄደ፡፡
ከዛ ከእነሱ ስለሚጠበቀው ነገር፤ ስለዋና ዋና የግቢው ህግ፤ማድረግ ስለሚገባቸው መድረግ ስለሌለባቸው ነገር የአንድ ሰዓት ገለፃ ከተሰጣቸው በኃላ ናኦል ወደ ወንዶች ህንፃ ኑሀሚም ወደ ሴቶች ህንጻ ተወሰድና ከሌላ ከአንድ ሰው ጋር የሚጋሩት የራሳቸው መኝታ ቤት ተሰጣቸው፡፡በዚህ ሁኔታ አዲሱን ህይወታቸውን አህዱ ብለው ጀመሩ፡፡
ወደእዛ ግቢ ገብቶ በቃችሁ ውጡ ከመባሉ በፊት ለመውጣት መሞከር መጨረሻው ሞት ብቻ እንደሆነ ያወቁት ግቢውን በረገጡ በቀናቶች ውስጥ ነበር፡፡እንደተባለውም ስልጠናው የተለየ እና በእነሱ ዕድሜ ደረጃ ላለ ወጣት ይቅርና ለሙሉ ወጣትም የማይሞከር ነበር….ግን ስልጠናውን በቃኝ አልቻልኩም ማለት እራስን ለሞት አሳልፎ ከመስጠት ውጭ ሌላ የሚያሰገኘው ነገር የለም፡፡ስለዚህ የማይቻለን መቻል የግዳቸው ነበር፡፡ወታደራዊ ስልጠናው ብቻ ሳይሆን መደበኛ ትምህርቱ እራሱ በጣም ጥብቅ በሆነ ስነምግባር የሚሰጥ ነበር፡፡አንድ ልጅ እዛ ግቢ ሲገባ ሶስተኛ ክፍልም ይሁን ስድስታኛ ክፍል የ5 አመቱን የሥልጠና ጊዜ ጨርሷ ከዛ ጊቢ ተመርቆ ሲወጣ የ12ተኛ ክፍል ማትሪክ ወስዶ መሆን አለበት ፡፡በዛ የተነሳ በአመት ሁለት ክፍሎችን መማር የግድ ይላል፡፡ደግነቱ የትምህርት አሰጣጡ እጅግ ዘመናዊና ሁሉ ነገር የተሞላለት አስተማሪዎቹ ልክ እንደእነሱ በልዩ ችሎታቸውና ብቃታቸው የተመረጡ ጂኒዬሶችና ነገሮችን በቀላሉ በማስረዳት ችሎታቸው የተመሰከረላቸውና ስለሆኑ ጫናዎቹ የሚጠበቀውን ያህል እንዳይከብዳቸው ያግዛቸዋል፡፡በዛ ላይ እያንዳንዱ ሰልጣኝ እንደ ዝንባሌው በተለያዩ የስፖርት አይነቶቹ መሳተፍና የቋንቋ ስልጠናውም በተመሳሳይ ሁኔታ መውሰድ ይጠበቅበታል፡፡በተለይ ከውጭ ቋንቋ እንግሊዘኛና አረብኛ ሲማሩ ከሀገር ውስጥ እንደየ ምርጫቸው ከሚያውቁት በተጨማሪ ሁለት ቋንቋ እንዲማሩ ይደረጋል፡፡
ይሄ በሀገሪቱ የደህነነት መስሪያ ቤት በልዩ ፕሮጀክት እቅድ ተነድፎለት በጀት ተይዞለት እየተካሄደው ያለው ልዩ ስልጠና ለመጀመሪያው አንድ አመት ለሁሉም ተማሪዎች በጣም ከባድ አካልንም መንፈስንም በእኩል ደረጃ የሚያዝል ነበር፡፡ለዚህም ማሳያ በተቀመጠው ክራይቴሪያ ከተለያ ቦታ በተለያየ ዘዴ ተሰብስበው ከገቡ 80 ተማሪዎች መካከል በአመቱ መጨረሻ 17 ቱ መቋቋም አቅቶቸው ሞተው ነበረ፡፡ናኦልም እህቱ ከጎኑ ኖራ በየጊዜው ብርታት ባትሰጠው ኖሮ ከሞቾቹ መካከል መሰለፉ አይቀርም ነበር፡፡ለዚህ ነው መጀመሪያውኑ ሰልጣኞቹ ሲመለመሉ  አስፈላጊው ክራይቴሪያ ዘመድና ጠያቂ የሌላቸው እንዲሆኑ የሚፈለገው፡፡
ኑሀሚ ግን ከሶስት ወር በላይ አልተቸገረችም ነበር….ካዛ በኃላ በየዲሲፕሊኑ ከፉክከሩ መድረክ ከፊት የምትሰለፍ፤ ለሁሉም ሰልጣኞች ምሳሌና ብርታት ሆና ነበረ የቀጠለችው፡፡አመስት አመቱ አልቆ ሲመረቁ ከአንድ ወንድ ጋር በእኩል ነጥብ አንደኛ በመሆን የወርቅ ዋናጫውን ተቀበለች፡፡ወንድሟ ናኦል 53 ተኛ ወጥቶ ተመረቀ፡፡እና 5 አመት ከኖሩበት ከእዛ ማሳልጠኛ ውስጥ ልክ እንደአገባባቸው በጨለማ መኪና ውስጥ ተሳፍረው እንዲወጡ ተደረገ.፡፡ከሰዕታት ጉዞ በኃላ ግን ልክ መስቀል አደባባይ አካባቢ መኪናዋ ቆማ ስታወርዳቸው የተቀበለቻቸው ምስራቅ ነበረች፡፡
በወቅቱ ሁለቱም ያለልዩነት ነበር የተጠመጠሙባት፡፡እሷም በደስታ እና በከፍተኛ እርካታ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡ስታያቸው ከበፊቱ በጣም አድገው ሙሉ ወጣት ሆነው ስላየቻቸው እጅግ ተደስታ ነበር፡፡ከዛ መኪና ውስጥ አስገባቻቸውና ቀጥታ ወደወላጆቻቸው ቤት ነበር የወሰደቻቸው፡፡ከመኪና ስትወርድ አብረዋት ወረዱ…ሰፈሩን ሲያዩና የቆሙበትን ሲረዳ ሁለቱም ደንዝዘው ነበር..ቀጥታ ሁለቱንም መሀከላቸው ገባችና ግራና ቀኝ እጃቸውን ይዛ ወደ ግቢው በራፍ ይዛቸው ሄደች…ሁለቱም በዝምታና በድንዛዜ ተከተሏት..ካዛ አንኳኩታ ሰውዬው ሲወጣ የሆነ ነገር ትለዋለች ብለው ሲጠብቁ..ኪሶ ገባችና ቁልፍ በማውጣት..‹‹ይሄው ቃል በገባሁት መሰረት የወላጆቻችሁ ቤት ቁልፍ ››ብላ ኑሀሚ እጅ ላይ አስቀመጠችላት፡፡ኑሀሚ አላመነችም፡፡ በድንዛዛ እጇን አንቀሳቀሰችና ቁልፉን ከፈተች.. አሸከረከረች… ተከፈተ.. ተንደርድራ ወደውስጥ ገባች፡፡ ወንድሟም ተከተላት፡፡ በረንዳው ላይ እስኪደርሱ አልቆሙም…የሳሎኑን በራፍ ስትገፋው ተዘግቷል፡፡ እጆ ላይ ባለው ቁልፍ ሞከረች ፤ተከፈተ……፡፡ በእንደዚህ አይነት ሁኔታ እነሱ ምንም ሳይለፉና ሳይጥሩ ነበር በምስራቅና በደህንነት መስሪያ ቤቱ ጥረት የወላጆቻቸው ቤት የተረከቡት፡፡
ከዛ ሁለት ወር ሰይቆይ ኑሀሚ በስልጠናዋ ባስመዘገበችው ብቃት ምክንያት ለተጨማሪ የሶስት አመት ስልጠና ወደ ራሺያ ተላከች፡፡
ናኦል ደግሞ ቤተሰቦቹ ቤት እየኖረ አዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ገብቶ ትምህርቱን እየተማረ በተደራቢነት ከምስራቅ  በሚሰጠው መመሪያና ተልዕኮ መሰረት የፊልድ ስረዎችን እንዲላመድ ተደረገ፡፡
ናኦል ከትዝታው ባኖ ግድግዳው ላይ የተለጠፈውን ሰዓት ሲያይ በጣም ነበር የተገረመው….ከለሊቱ10፡20 ሆኗል …ላለፉት አራት ሰዓት በላይ ባለፈ ታሪኩ ውስጥ ሰምጦ በትዝታ ሲዋልል ነበረ፡፡አካሉም ብቻ ሳይሆን አእምሮውም ዝሏ ነበር ፡፡
/////
ኮሎምቢያ/አሞዞን ደን ውስጥ
ካርሎስ ከጥልቅ እንቅልፉ ባነነ እና አይኖቹን ገለጠ፡፡በድቅድቁ ጨለማ በአማዞን ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ግዙፍ ዛፍ ላይ ቆንጆና ወጣት ልጅ ደረቱ ላይ ተኝታ ነው ያገኘው…ያለበትን ሁኔታ አሰበና ፈገግ አለ፡፡ቀስ ብሎ ከደረቱ ላይ ቀና አድርጎ ሲያስነሳት ነበር ከገባችበት ጥልቅ ትዝታ የነቃችው፡፡
‹‹ወይ ሀሳቤን ጥዬ ተንፈላሰስኩብህ አይደል?››አለችው፡፡

‹‹አይ የተፈጥሮ ጥሪ አጨናንቆኝ ነው››

‹‹ማለት?››

‹‹ሽንቴን…ኩላሊቴ ልትፈነዳ ነው››

‹‹እ ..ነው..ወርደህ ልትሸና ነው?፡፡

‹‹አይ ምን አስወረደኝ..ብወርድ ሽንት ቤት የለ ..ሜዳ ላይ ነው የምሸናው፡፡ ማይደብርሽ ከሆነ እዚሁ ሆኜ ልለቀው ነው፡፡››
በጨለማ ውስጥ የማይታየውን ፈገግታዋን እየለገሰችው‹‹ምን ቸገረኝ..ልቀቀው.››አለችው

‹‹አመሰግናለው ››አለና ቆመ፡፡ ዚፕን መክፈት ሲጀመር.

‹‹እንዴ…››ብላ አጉረመረመች

‹‹ምነው?››

‹‹ቢያንስ ፊትህን ወደእዛ አዙር እንጂ››

ከመጽሐፍት መንደር💠

09 Nov, 17:25


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-19
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

///
ምስራቅ ኮስተር ብላ‹‹አትልፈስፈስ…ጠንከር ብለህ መሆን ስለሚገባው ነገር ብቻ እንነጋር፡፡››አለችው፡፡

ናኦልም‹‹ምን የሚሆን ነገር አለና እንነጋራለን…በዚህ ምድር ላይ አንድ አለቺኝ የምላት እህቴን እንዲህ ባለ ሁኔታ አጥቼያት እኔስ በህይወት መኖሬን ቀጥላለው?››ስል መለሰላት፡፡
‹‹አይዞህ ኑሀሚ እንደዚህ ካሉ ብዙ አደጋዎች ሰርቫይቭ የማድረግ ልምድ ያላት ልጅ ነች፤ደግሞ በምድር ላይ ያለችህ እሷ ብቻ አይደለችም..እኔም እኳ ስላለሁ መሰለኝ አሁን በዚህ የሀዘንህ ወቅት አጠገብህ ያለሁት፡፡
‹‹እሱማ እውነትሽን ነው፡፡››
‹‹እኮ ..በል ተነስና መልስ እንመልስለት፡፡››
ከተዘረፈጠበት ተነሳና ወደእሷ ቀረበ‹‹ምን ብለን?››
‹‹ያልከኸውን አደርጋለው..ለማንም ሳልናገር ያልከው ሀገር ድረስ እመጣለሁ..ግን እህቴ በህይወት መኖሯን በምን አውቃለሁ?አንድ ማረጋገጫ ስጠኝ፡፡››
‹‹አዎ እንደዛ ብንለው ይሻላል አይደል…?ወይ ተጨማሪ ፎቶ ወይ ቪዲዬ ይልክልናል፡፡ወይ ደግሞ በስልክም ሊያገናኘን ይችላል፡፡››
‹‹በቃ ራስሽ ፃፊው››

እንደማሰብ አለችና ፃፈችና ላከች፡፡መልስ እስኪመጣ ለመጠበቅ ተያይዘው ወደሳሎን ሄዱ፡፡ለሁለቱም የሚጠጣ ቢራ አቀረበና እሱን እየጠጡ በትካዜ በስልኩ ከአሁን አሁን የሚላከውን ኢሜል መጠበቅ ቀጠለ፡፡
ከሶስት ሰዓት በኃላ ተጨማሪ ፎቶ ተላከላቸው፡፡እንሱ ያላወቁት እነዛ ፎቶዎች የተመረጡት ከኑሀሚ ስልክ ውስጥ በፔሩ ቆይታዋ በተያዩ ጊዜያቶች ከተነሳቸው ውስጥ የተመረጡትን ነው፡፡
ከፎቶ ጋር አጭር መልዕክት ተልዕኮል
‹‹ባቀረብንልህ ሀሳብ ከተስማማን አሁኑኑ አሳውቀን፡፡››ይላል፡፡

‹‹እ ምን አሰብሽ? ››አለት፡፡ ከምስራቅ የተሻለ ሀሳብ ለማግኘት እየተመኘ ጠየቃት.. ምርጫ የለንም ‹‹ተስማምቼያለሁ ብለህ ላክላቸው፡፡››እንዳለችው አደረገ፡፡
በል የጉዞ ሰነዶችህን አዘጋጅ…በሶስት ቀን ውስጥ አስፈላጊውን ገንዘብ ስለምንልክልህ ሙሉ ስምህን እና አስፈላጊ መረጃዎችን ላክልን፡፡እንደተነጋገርነው ግን ይሄንን ሚስጥር ሌላ ለሶስተኛ ወገን ለመንግስት አሳልፈህ ብትሰጥ ነገሮች ሁሉ ያከትምላቸዋል….ከዛ በኃላ
እህትህን በዚህ ምድር ላይ ዳግመኛ የማግኘት እድልህ ከዜሮ በታች ይሆናል…በል ፍጠን ይላል፡፡
‹‹አነበብሽው አይደል?››
‹‹አዎ ..አነበብኩት..››አለችና ከተቀመጠችበት ተነሳች፡፡
‹‹ምነው? ››
‹‹ልሄድ ነው፡፡››
‹‹ልሄድ ነው በእንደዚህ አይነት በተሰባበርኩበት ሁኔታ ላይ ሆኜ ጥለሺኝ ልትሄጂ ነው….፡፡››
‹‹ጎረምሳው ተረጋጋ እንጂ ..ይልቅ እራስህን ለረጅምና አስቸጋሪ ጉዞ አዘጋጅ፡፡እኔ ሄጄ ለጉዞ አስፈላጊ የሆኑ ፖስፖርትና ቢዛዎችን ላዘጋጅ፡፡ ታውቃለህ እነዚህን የጉዞ ሰነዶች በአሁኑ ጊዜ በስድስት ወር ውስጥም ማግኘት አይቻልም፡፡አኔ ደግሞ ከሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማግኘት

አለብኝ፡፡ ለዚህ ደግሞ ደቂቃዎችን ሳላባክን ከአሁን ያለኝን ኃይልና መስመር ሁሉ ተጠቅሜ ማሳካት መቻል አለብኝ…እ ምን ትላለህ ጎረምሳው?››
ተንደረደረ ሄደና ተጠመጠመባት፡፡እሷም እጆቾን በአንገቱ ዙሪያ ጠመጠመቻቸው… ጭምቅ አደረጋት፡፡
‹‹አንቺ ስላለሺኝ ሁሌ ደስተኛ ነኝ፡፡ዘላለም በእቅፍሽ ውስጥ መኖር ነው ምኞቴ…በጣም ነው የምወድሽ….››አላት
‹‹….ተራጋጋ፡፡ከዚህ በላይ ከወራን እንባዬ ያመልጠኛል፡፡››አለችና ከእቅፉ ወጥታ ፈዞ በቆመበት ፊቷን አዙራ ወጥታ ሄደች፡፡በቦዘዙ አይኖቹ በስስት እያያት በሀሳቡ ሸኛት፡፡..
///

ከሶስት ቀን በኃላ በአለምአቀፍ የሀዋላ አስተላላፊዎች አማካይነት 50 ሺ ዶላር ተላከለት፡፡ያልጠበቀው ነገር ነበር፡፡ብሩ ሲደርሰው ነገሩ ሲሪዬስ እንደሆነ እሱ ብቻ ሳይሆን ምስራቅም ተገነዘበች፡፡ሁለቱም መመለስ ያቃቸው ይሄ ሁሉ አጋቾቹ ይሄን ሁሉ ኢንቨስትመንትና ጥረት የሚያደርጉት ከእሷ ምን ፈልገው ነው? የሚለውን ነው ፤የእሱንስ ወደፔሩ መሄድ ለምን ፈለጉት?››በተለይ ይሄን ጥያቄ ከአንደበቷ አውጥታ ለእሱ አትንገረው እንጂ ምስራቅንም በጣም ነው ያሳሰባት፡፡
ናኦል ገንዘቡ እንደደረሰው ካወቀ በኃላ እንቅልፍ ሊወስደው አልቻለም፡፡ሰዓቱ ገፍቶ ከለሊቱ ስድስት ሰዓት ሆኖኛል በተኛበት አልጋ ላይ እየተገላበጠ በትዝታ ወደኃላ ወደልጅነታቸው ተጓዘ፡፡ምስራቅ እሱና ተወዳጅ እህቱን ከጎዳና አንስታ እንዴት ሰላይ እዳደረገቻቸው በዝርዝር ትዝ አለው፡፡
ከ15 አመት በፊት ምስራቅ የወንድሜ ቤት ነው ብላ ከጓዳና አንስታ ጎተራ የሚገኝ ኮንደምንዬም ቤት ከወሰደቻቸው በኃላ ከአዛው ቤት ሳይወጡ ሁለት ወር ሙሉ ቆይተው
ነበር፡፡ በሶስተኛው ወር ግን ማታ እራት በልተው ቴሌቬዥን እያዩ እያለ ድንገት ሪሞቱን አንስታ ቴሌቪዝኑን አጠፋችና ፊት ለፊታቸው ቁጭ አለች፡፡
እህትና ወንድም እርስበር ተያዩ ፡፡የሆነ ነገር ልትነግራቸው እንደሆነ ገብቷቸዋል፡፡፡ግን የጠረጠሩት በቃ እስካሬ ለሁለት ወር በምቾትና በድሎት በወንድሜ ቤት አኑሬያችኋለው፤ ከአሁን በኃላ ግን ምትኖሩበት ቦታ ፈልጉ ›› ትለናለች ብለው ነበር የጠበቁት፡፡ይሄንን ጉዳይ እሷ ቤት በማትኖርበት ጊዜ እያነሱ ተወያይተውበታል..ለዛ ነው በፍጥነት ወደሁለቱም ምናብ ሀሳቡ የመጣው፡፡
‹‹ልጆች በጣም እንደምወዳችሁ ታውቃላችሁ አይደል?››

‹‹አዎ እናውቃለን፡፡ እኛም በጣም እንወድሻለን››ሲል የመለሰላት ናኦል ነበር፤ኑሀሚ ግን ይሄንን ቤት ለቀው ከወጡ በኃላ ምን ማድረግ እንዳለበባቸው ስታሰላስል ነበር፡፡ደግማኛ ወንድሟን ይዛ ወደበረናዳ ለመመለስ ፈፅሞ ፍቃደኛ አልነበረችም፡፡ትንሽም ቢሆን የራሳቸው ቤት ተከራተው መኖር እንዳለባቸው ከወሰነች ሰነባብታ ነበር፡፡ለዛ ኪራይ ቤት ክፍያ ሚሆን ገንዘብ ለማግኘት ደግሞ ማንኛውንም ስራ ለመስራት ፍቃደኛ ነበረች፡፡ ለወንድሟ ስትል ብትሰርቅም ብትገድልም ግድ አልነበራትም፡፡
ምስራቅ ንግግሯን ቀጠለች‹‹ይሄውላችሁ ምን መሳላችሁ…አንደእኔ እንደእኔ ዘላለም እዚሁ አንድ ላይ እንዲህ እየተሳሰብን በፍቅርና በደስታ መኖር ብንችል ደስ ይለኝ ነበር… ግን ያው ታውቃላችሁ አይደል?››
ቀጥታ ወደጉዳዩ ገባች‹‹ማለት የምትፈልገውን ፍርታ ማለት ባለመቻሏ ሁለቱም ላይ ጭንቀት ፈጠረች…ኑሀሚ ፈጠን አለችና‹‹ይገባናል..እስከዛሬ ስለተንከባከብሽንና በዚህ ሁኔታ እንድናገግምና ስለወደፊታችን እንድናስብ ስላደረግሽን የላለም ባለውለታችን ነሽ፤ግን ወንድሜን ይዤ ወደበረንዳ መውጣት አልፈልግም…ከቻልሽ ለእኛ ምትሆን ትንሽ ቤት
ተከራይተን መኖር እንድንችል አግዢን፡፡ማንኛውንም ያገኘነው ስራ በመስራት የቤት ኪራዩን በመክፈል እራሳችንን ማኖር አያቅተንም…እቤት ካገኘን ነገ ተነገ ወዲያ እንሄዳለን..አንቺ አታስቢ››
ምስራቅ ፈገግ አለች‹‹እንዳዛ ማለቴ አይደለም፡፡እኔ እንደምታዩት እዚህ የምኖረው ብቻዬን ነው፡፡ ቤቱም ሰፊና ለሁላችንም የሚበቃ ነው፡፡እዚህ ከእኔ ጋር በመኖራችሁ በጣም ተጠቃሚው እናናተ ሳትሆኑ እኔ ነኝ….ግን ለእናንተ የወደፊት ህይወት ሲባል የተለየ መንገድ መከተል አለብን፡፡››
ሁለቱም  ስሜታቸው  ይበልጥ  ተናቃቃ፡፡የምትላቸው  በፍፅም እየገባቸው  አይደለም፡፡
‹‹አልገባንም›› አለች..ኑሀሚ

ከመጽሐፍት መንደር💠

09 Nov, 15:49


እንደምን አመሻችሁ አንድ ነገር ላስቸግር ነበር የሆነ ቅኔ ፍታ ተብዬ ተልኮልኝ ከበደኝ የሚያግዘኝ አለ ጉባኤ ቃናንን ማለት ልክ እንደ ዋሸራ 🙏🙏🙏

ከመጽሐፍት መንደር💠

08 Nov, 19:25


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-18
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ደቡብ ኮሎምቢያ/የአማዞን ደን
ደግላስ አንድ ወር ከራቀበት የግል ግዛቱ ሲመለስ ፍፁም የሆነ ደስታ ነው የተሰማው፡፡ከመኪናው ወረዶ የቅፅር ግቢውን አፈር እንደረገጠ በውስጡ ጎድሎ የነበረው ኀያልነቱ መልሶ ሲሰርግበት ተሰማው፡፡አፉን በደንብ ከፈተና አየሩን ወደውስጥ ምጎ በመሳብ በአፍንጫው አስወጣው፡፡.አሁን ያለበት የግል ግዛቱ የሆነው እንደቤተመንግስቱ የሚያየው ስፍራ አስር ሺ ካሬ ላይ ያረፈ ቅፅር ግቢ…ወደ ሰሜን አቅጣጨ ጠጋ ብሎ በአንድ ሺ ካሬ ሜር ላይ ያረፈ ግዙፍ ባለአንድ ፎቅ ህንፃ ሲኖር.. ህንፃው….ከመሬት በታች አንደርግራውንድ ቤት ሲኖረው ሙሉ በሙሉ መግቢያው በጀርበ በኩል ሚስጥራዊ መሹለኪ ሆኖ የተዘጋጀ ነው፡፡ በውስጡ ሀያ የሚሆኑ ሳይንቲስቶች ከነረዳቶቻቸው ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ያለእረፍት ይሰሩባታል፡፡ ምን አልባትም በአለም ግዙፍ የተባለው የኮኬይን ቅመማ የሚካሄድበት የተሞላ የላባራቶሪ እቀዎች የተተከሉበት….በየወሩ አንድ 100 ኩንታል ኮኬይን ተቀምሞ፤ ተመርቶና በተለያየ መጠን በጥንቃቄ ታሽጎ በኮሎምቢያ …ፓናማና… ሚክሲኮን በመሸገር በአሜሪካ የሚገባበትና የሚሰራጭበት እስከአውሮፓ የሚዘልቅ  ሰንሰለት ያለው ውስብስብ ስራ ነው፡፡
ኮኬይኑ እዛ ደርሶ ከተሰራጨ በኃላ ከሽያጩ ሚሰበሰበው ረብጣ ዶላል ለሁሉም ተወናዬች የየድርሻቸውን በማክፋፈል የቀረውን ዳጎስ የለ ድርሻ ለዳግላስ ተመልሶ የሚመጣበት አሰራር ነው ያለው፡፡ዳግለስ ለዚህ የኮከዬን ምርት ሚሆነውን የኮካ ዛፍ ምርት የሚያገኘው እዚሁ አሁን ካለበት ተያይዞ ካለ መቶ ሺ  ካሬ ሜትር የእርሻ መሬት ነው፡፡ቀሪውን 60 ፐርሰንት ግን ከአካባቢው በቅርብ ርቀት ላይ በአማዘን ደን ወስጥ ሆነ ከዛ ውጭ ተበትነው በሚገኙ ከግለሰብ ሆነ ከብድን እምራቾች ጋር በፈጠረው የንግድ ስምምነት ይሰበስብና ጉድለቱን ያሟላል፡፡
ይሄን ጥሬ እቃውን ከእርሻ ቦታም ሆነ በክፍያ ከሚሰበሰብበት ቦታ የሚሰበበስቡ እንዲሁም የቢዝነሱን ሆነ የእሱን ድህነንት የሚጠብቁ…ግደሉ ሲላቸው የሚገድሉ፤ ሙቱልኝ ሲላቸው የሚሞቱላት በሺዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች አሉት፡፡የህንፃው ግራውንድ ላይ ደግሞ እታች ቤዝመንት ውስጥ ለሚሰሩት ሳይንቲቶችና ዋና ዋና የታጣቂ አዛዦች መኖሪያነት ያገለግለል፡፡ከላይ ያለው የመጀመሪያው ፍሎር ግን ለደግላስ የግል ቤተመንግስቱ ነው፡፡አንድ ግዙፍ ሳሎን፤30 የሚሆኑ መኝታ ቤቶች፤ከአምስት በላይ ቢሮዎችና በአጠቃላይ ከ50 በላይ ክፍሎች ከነቅንጡ እቀዎች ያሉበት ዘመናዊ ቤት ነው፡፡እዛው ቤት ውስጥ ደግላስና አንድ ወንድ እና ሁለት ሴት አገልጋዬቹ ብቻ ናቸው የሚኖሩበት፡፡ከዛ ውጭ እሱ ኖረም አልኖረም ሳይፈቅለድት ወደ እዛ ህንፃ ለመውጣት የሚደፍር ሰው የለም፤ካለም በደግላስ ጥይት ወይ ግንባሩ ይፈረከሳል ወይ ደግሞ ደረቱ ይነዳላል፡፡
ሌላው የህንፃ ጣሪያ ከላይ እይታ እንዳይስብ  አረንጓዴ ሳርና ቋጥኝ መሰል ተክሎች እንዲለብስ ተደርጎ ሙሉ በሙሉ እይታው ከአማዞን ደን ጋር እንዲመሳሰል ተደርጎል፡፡
የዳግላስን ወደቤቱ መምጡት አስመልክተው በስልፍ ሆነው የእንኳን በሳላም መጣህ አቀባበል ሊያደርጉለት እየጠበቅ ያሉትን ታጣቂዎችና ሌሎች ሰረተኞችን ቀላል እና አጭር ሰላምታ ሰጠና ቀጥታ አንደኛ ፎቅ ላይ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤቱ ሔደ፡፡ከዛ ወደዋናኛ መኝታ ቤቱ ነው የገባው፡፡አሁንም ያቺ ጠፋች የተባለችው ኢትዬጵያዊት ሴት በአእምሮው እየተመላለሰች ነው፡፡እሷን እንዳገኞት እስክያበስሯት ድረስ ተረጋግቶ ስራውን በስርአት መስራት እንደማይችል ገብቶታል፡፡ደህንነቱ የተጠበቀ የመገናኛ ስልኩን አወጣና መልሶ ላንቲኒያ ወደሚገኙ የእሱ ሰዎች ደወለ ‹‹እሺ አዲስ ነገር አለ?››
‹‹ሁሉንም ሰው አስማሪቼለው..እስከአሁን አዲስ ነገር አላገኘንም፡፡››

‹የልጅቷ እቃዎች አሉ?››ሲል ያልጠበቀውን ጥያቄ ጠየቀው፡፡
‹‹የእጅ ቦርሰዋን ይዛ ነው  የሄደችው… የልብስ ሻንጣዋ ግን አሁንም ከእኛ ጋር ነው፡፡››
‹‹ውስጡ ምን አለ?››

‹‹እኔ እንጀ! እስከአሁን ከፍተን አላየነውም፡፡››

‹‹ክፈተው››

‹‹እሺ…››

ከተወሰነ ደቂቃ ዝምታና መተረማመስ በኃላ…‹‹ሻንጣው ተቆልፏል እንዴት ላድርግ?››የሚል ቃል ተሰማ፡፡
‹‹አንተ ጀዝባ …ስረህ አልመሆኔ በጀህ እንጂ በዚህ ጥያቄህ ግንባርህን ነበር የመነድልልህ…በጩቤ ዘንጥለህ ክፈተው››አንቦረቀበት፡፡
እንዳለው ከጎኑ የሻጠውን ጩቤ አወጣና የኑሀሚ ሻንጣ ከጉን በኩል ቦትርፎ ከፈተው፡፡ ውስጥ ያለውን እቃ እንዳለ ወለሉ ላይ ዘረገፈ…ቀሚሶች..ጅንስ ሱሪ…ፓንቶች…ጡት ማስያዣ… ማስተወሻ ደብተር……በቀ ይሄው ነው ያለው፡፡››
‹‹በቃ..››በብስጭት ጠየቀ
‹‹አዎ ..ቆይ…ሌላ አንድ አይፓድ አለ፡››

‹‹አዎ እንደእሱ አይነት እቃ ነው የምፈልገው…ክፈተው፡፡››

‹‹እ››ብሎ ለመክፈት ማከረ..ግን አልሆነለትም፡
‹‹አበራሁት …ግን ልከፍተው አልቻልኩም… ፓስ ወርድ አለው››

‹‹በቃ..በቃ አሁኑኑ..ተነስና ለሊቱንም ተጉዘህ ወደእኔ ይዘኸው ና…..ጥዋት ከእንቅልፌ ስነሳ አይፓዱን ካላገኘው..በቃ ሟች ነህ››አለና ስልኩን ዘጋው፡፡
ታጣቂው ወዲያው ነበር ጊዜ ሳያባክን አይባዱን እና የቦተረፈውን ሻንጣ መልሶ ከፍቶ እቃዎችን ወደውስጥ በመመለስ ይዞ ከአካባቢ ገበሬ አንድ ፈረስ ተውሶ ዳግለስ ወደሚገኝበት ሳንቹዋሪ ሽምጥ መጋለብ የጀመረው፡፡
ዳግላስ ጥዋት በጠበቀው ሰዓት አይፓዱ ደረሰው፡፡ እዛው የእሱ ሰረተኛ በሆነ የኮምፒተር ባለሞያ ሀክ አስደርጎ ፓወርዱን ካሰበረ በኃላ ውስጡን ማየት ጀመረ፡፡
የፎቶ አይነት ..እርቃኗን የተናሳችውን ጭመር ..ቪዲዬዎች..፡፡አብዛኛዋቹ ፎቶዎቸና ቪዲዬዎቸ በእሷ አድሜ አካባቢ ካለ ወጣት ጋር አብራ ስትስቅ ..አልያም እላዩ ላይ ተንጠልጥላበት..አዝላው ወይም አዝሏት የተነሱት ወይም የተቀረፁት ነው፡፡ፍቅረኛዋ እንደሆነ እርግጠኛ ሆነ፡፡አይፓዱን ከኢተርኔት ጋር አገናኘና የተላኩላትን ብዙ መልእክቶች ተመለከተ፡፡ግን በማያውቀው ቋንቋ ስለሆነ መረዳት አልቻለም፡፡ወደጎግል ገበና የኢትዬጵያ ብሄራዊ ቋንቋ ምን እንደሆነ ጠየቀ፡፡አማርኛ የሚል መልስ አገኘ፡፡አማርኛ የሚባል ቋንቋ መኖሩን እራሱ አያውቅም ነበር፡፡የሀገሬው ቋንቋ እንደሆነ ተረድቷል፡፡ በጣም ነው የተገረመው፡፡በደቡብ አሜሪካ ያሉትን ሀገሮች አሰበ…ፔሩ ፤ኮሎምብያ፤ አርጀንቲና ብሄራዊ ቋንቋቸው እስፓኒሽ ነው..ብራዚል በፖርቹጊዝ ቋንቋ ነው የምትገለገለው፤ኢጎና እንግሊዘኛ ነው ..እንደዛ እያለ ይቀጥላል፡፡ቢያስብ ቢያስብ አንድም ሀገር የራሱን ቋንቋ ብሄራዊ ቋንቋው አድርጎ የሚጠቀም ሊያስታውስ አልቻም፡፡ሀሳቡን ተወና ጎግል ትራንስሌት ከፍቶ መልእክቶቹን ኮፒ ፔስት እያደረገ ከአማርኛ ወደ እንግሊዘኛ በመቀየር ለመረዳት ሞከረ፡፡በጣም ነው የተገረመው፡፡ያ ሁሉ መልእክት ከወንድሟ እንደነበረ..እና እሷ በመጥፋቷና አድረሻዋን ሊያገኝ እንዳልቻለ በመጨነቅ በተደጋገሚ ጊዜ የላከላት መልእክት ነው፡፡…ፍቅረኛዋ ነው ብሎ ያሰበው ወንድሟ መሆኑን ሲያውቅ ደስ አለው፡፡በዚህ መጠን የሚተሳሰቡና የሚወደዱ ወንድም እና እህት  መኖራቸውን  ተጠራጠረ…የእሱን  የራሱን  ወንድምና   እህቶች   አሰበና በመሀከላቸው ያለውን መግባባትና ፍቅር መዝኖ ፈገግ አለ፡፡በዘ ቅፅበት ያላሰበው ተንኳል በአእምሮ ብልጭ አለበት፡፡ይህቺ ሴት አምልጣ የመንግስት ተቋም ያለበት አካባቢ በህይወት መድረስ ብትችል እንኳን

ከመጽሐፍት መንደር💠

06 Nov, 18:30


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-17
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ደረቱ ላይ እንደተጋደመች..አይኖቾን ጨፍና ሀሳብ ውስጥ ገባች…በትዝታ ወደሚስኪን ሀገሯ ተመለሰች፡፡እንዴት ለጀመሪያ ጊዜ ከጓዳና ህይወት እራሳቸውን እንዳላቀቁ ነው ትዝ ያላት፡፡
ከ15 ዓመት በፊት /ኢትዬጵያ/አዲስ አበባ/

መንትዬዎቹ ከኩማደሩ ቢሮ እንደወጡ ቀጥታ ተንደርድረው ፊት ለፊት ያገኙት ካፌ ነበር የገቡት፡፡ሁለቱም ምሪንደ አዘው ውስጣቸውን እያቀዘቀዙ ለበርካታ ደቂቃዎች ያለንግግር በየራሳቸው እያወሩ አሳለፉ…
‹‹ወንድሜ ..ተይዘን ቢሆን ኖሮ የሆነ ነገር ያደርጉብኛል ብዬ በጣም ሰግቼ ነበር….››

‹‹እንዴ ትቀልጂያለሽ እንዴ? ተይዘን ቢሆን ኖሮኮ ሁለታችንንም ነው የሆነ ነገር የሚያደርጉን..ወፌ ላላ ሁሉ ሊገርፉን ይችሉ ነበር…፡፡››ሲል መለሰላት
‹‹አውቃለሁ…ግን እኔ እችለዋለው..አንተን ግን በጣም ያምሀል››አለችው፡፡ አሁን የሆነ ይመስል በሰንበር የበላለዘ ጀርባውንና የቆሰለ ሰውነቱን በምናቧ እያይች ዝግንን አላት፡፡
‹‹አይ እህቴ ..አንዳንዴ እናቴ የሆንሽ ነው የሚመስለኝ..የ0 ደቂቃ ታላቅ ወንድምሽ መሆኔን ዘነጋሽው እንዴ?ለማንኛውም አሁን ስራችንን በስኬት አጠናቀናል፡፡ብዙ ገንዘብም አግኝተናል፡፡›
‹‹አዎ እሱ ጥሩ ነገር ነው….››
‹‹አዎ ..ጥሩ ነው ደጋግማ እንዲህ አይነት ስራዎችን እያሰራች እንዲህ ብዙ ብር ብትከፍለን በጣም ደስ ይለኝ ነበር…››
‹‹እስኪ መጀመሪያ የሰራንበትን ቀሪ ሂሳባችንን ትስጠን››
‹‹አረ ኑሀሚ…አሁንም ያቺን ልጅ ኣታምኚያትም ማለት ነው?››

‹‹ለምን ብዬ አምናታለው…ወላጆቼ ሰው በማመን ምን አተረፉ..ይገባሀል እኔ በዚህ ምድር ላይ ካንት በስተቀር ማንንም ሰው ማመን አልፈልግም››አለችው፡፡
‹‹በቃ አትቆጪ እንዳልሺ ይሁንልሽ..አሁን ሂሳብ ክፈይና እንውጣ፡፡››
‹‹ከብዙ ድፍን ብሮች መካከል አንድ ነጠላ መቶ ብር መዛ የሁለት ለስላሳ ሂሳብ ለአስተናጋጁ ሰጠችው፡፡ሂሳብን ቆረጠና መልሱን አመጣላት፡፡አምስት ብር ቲፕ አስቀመጠችለት..ናኦል ያደረገችውን አየና ፈገግ አለ…፡፡››
‹‹ምን ትገለፍጣለህ..እኛም ወግ ይድረሰን እንጂ፡፡ይሄን ያህል ብር ለሰው በቲፕ መልክ ስንሰጥ እኮ ይሄ የመጀመሪያ ቀን ታሪካችን ነው፡፡››አለችው፡፡
‹‹እሱስ እውነትሽን ነው፡፡ሳናስበው ታሪክ መስራት ጀመርን ማለት ነው?››በገረሜታ ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ..እየሰራን መሰለኝ፡፡››በዚህ ጊዜ ወደበረንዳቸው ተመልሰው ዘወትር የሚቀመጡበት ጥርብ ድንጋይ ላይ ጎን ለጎን ተቀምጠዋል፡፡…ያንን ሁሉ ብር በኪሳቸው አጭቀው ይዘው ብዙ ብዙ ቦታ ሄደው ዘና ማለት እየቻሉ እዛ መቀመጥ አልነበረባቸውም፡፡ለምሳሌ ፊልም ቤት ገብተው ፊልም ማየት የሁለቱም ምርጫ ነበር፡፡ካልሆነም እናትና አባታችው መቃብር ጋር ሔደው ዛሬ የሰሩትን አስደናቂ ጀብዱም ሊነግሯቸው ይችሉ ነበር፤ግን አላደረጉትም ፡፡ ምክንያታቸው ምስራቅ እነሱን ፍለጋ ወደቋሚ ቦታቸው ስትመጣ እንዳታጣቸው ነው፡፡ግን በቀላሉ የምስራቅ ዱካ ሊሰማ አልቻለም፡፡ቦታው ላይ ስድስት ሰዓት የተቀመጡ እስከስምንት ሰዓት አልተንቀሳቀሱም ነበር፡፡
‹‹ወንድሜ ይህቺ ልጅ አብርታናለች መሰለኝ፡፡››

ኑሀሚ የተናገረችው እሱም በውስጡ እያሰላለስለ የነበረው ነገር ስለነበረ ለስለስ ባለ ቃል‹‹ለምን እንደዛ አልሺ?››ሲል ጠየቃት፡፡
‹‹ይሄው እንደምታያት ቀረቻ….ጉዳዮ ከተፈፀመላት ለምን ብላ መጥታ ሁለት ሺ ብር ሙሉ ትሰጠናለች?››

‹‹ግድ የለሽም እንደዛ አታደርግም…ትንሽ እንጠብቃት፡፡››

‹‹አይ እኔ ደግሞ የምታደርገው ነው የሚመስለኝ…ጥዋት ሁለት ሺ ብር ብላን አልነበር..አይሆንም አራት አድርጊው ስላት…..አይሆንም ባይሆን ሶስት እንኳን ይሁን አላለችንም፡፡በአንዴ ነው የተስማማችው፡፡በወቅቱ እንደውም በውስጤ ምነው ስድስት ሺ ወይ ስምንት ሺ ባልኳት እያልኩ ነበር፡፡ግን ይሄው እሷ እኛን ለማበረታታት እና ስራዋን በሞራል እንድንሰራላት እንጂ እንደማትከፍለን ታውቅ ነበር፡፡

‹‹እና ተመልሳ አትመጣም እያልሺኝ ነው?››

‹‹አዎ እንደዛ ነበር ያሰብኩት ..ግን ተሳስቼያለሁ መሰለኝ››አለችው፡፡

ናኦል በእህቱ ንግግር ግራ ተጋባ..‹‹መቃዠት ጀመረች እንዴ?›› ሲል በውስጡ አልጎመጎመ፡፡
‹‹እህቴ አልገባኝም፡፡››

‹‹ያቹት መጣችልህ..››አለችው ከመንገድ ማዶ እየጠቆመችው፡፡

ናኦል በደስታ ፈንጥዞ ከተቀመጠበት ተነስቶ ቆመ…‹‹እውነትሽን ነው እህቴ? የታለች?››

ሱሪውን ያዘችና ወደታች እየጎተተች‹‹አረ ሼም ነው..ቁጭ በል፡፡ምንድነው እንዲህ መንሰፍሰፍ?እናትህ መሰለችህ እንዴ?››

ተመልሶ ቁጭ አለና.‹‹ነግሬሽ ነበር እኮ..እሷ እንደሌላው ሰው አይደለችም፡፡አትቀርም ብዬሽ ነበር…፡፡››
‹‹በቃ አፍህን ዝጋ እየቀረበች ነው፡፡››

ዝም አለና ሁለቱም አይኖቻቸውን እያቁለጨለጩ ስራቸው እስክትደርስ ይጠብቋት ነበር፡፡ምስራቅ እንደደረሰች በዝምታ መሀከላቸው ሰቅስቃ ገብታ ተቀመጠችና….‹‹እሺ ጩጬዎቹ እንዴት ሆነላችው?››ስትል ምንም ነገር እደማታውቅ ሆና ትጠይቃቸው ጀመር፡፡
‹‹አድርገናል…እንዳልሺን አስቀምጠናል፡፡››ሊያብራራላት ሞከረ፡፡
ኑሀሚ ኮስተር እንዳለች….‹‹ቀሪውን ብር ይዘሽ መተሻል››ስትል ጠየቀቻት፡፡
‹‹እህቴ ብሩ የት ይሄድብናል..?መጀመሪያ ስራውን በትክክል መስራታችንን ታረጋግጥና ቀስ ብላ ትሰጠናለች፡፡››በልምምጥ ሊያረጋጋት ሞከረ፡፡
‹‹አታርፍም እንዴ…በትክክል እንደሰራነውማ ገና ድሮ ነው ያወቀችው፡፡››በኑሀሚ ንግግር ምስራቅም ሆነች ወንድሟ ደነገጡ፡፡ናኦል..እነሱ ካልነገሯት እንዴት ታውቃለች ብላ ልታስብ እንደቻለች ስላልገባው ነው..ምስራቅ የደነገጠችው በልጅነቷ የአእምሮ ስልነት ስለተደመመች ነው፡፡
‹‹ማወቋን እንዴት አወቅሽ?››ሲል ጠየቀት፡፡
‹‹ነግረሺናል እኮ ..ዕቃውን እዛ ያስቀመጥነው አንቺ እዚ ሆነሽ ዛፓው የሚሰራውን ሁሉ ለመከታተል ነው፡፡አስቀምጠን እንደወጣን አንቺ ሰውዬውን መከታተል ጀምረሻል፡፡ያ ባይሆን ኖሮ ስትመጬ ፊትሽ ላይ ቁጣና ንዴት ይታይ ነበር፤አሁን ግን እርካታና ደስታ ነው የማነበው፡፡››አብራራችላት፡፡
ምስራቅ ኪሶ ገባችና የታጠፈ ብር በማውጣት ..‹‹ይሄው ሶስት ሺ ብር..አንድ ሺ ብሩ እንዳልሺው ስላስደሰታችሁኝ ቦነስ ነው፡፡››አለችና እጇ ላይ አስቀምጣላት…ከተቀመጠችበት ተነሳችና ናኦልን በፍቅር ጭንቅላቱን በመነቅነቅ ቀጥ ብላ ተለይታቸው ሄደች፡፡
‹‹ምስራቅ…መች ነው የምትመጪው?››ጮክ ብሎ ጠየቃት፡፡
‹‹እዛ ቆቆር ቤት ወስደህ ቁርስ ምትጋብዘኝ ከሆነ ነገ ጥዋት እመጣለው፡፡››አለችው፡፡ ደስ ብሎት‹‹እጋብዝሻለሁ..እንዳትቀሪ፡፡››አላት ፡፡
‹‹እሺ አልቀርም፡፡››አለችውና ከእይታው ተሰወረች፡፡
ምስራቅን በአይኖቹ እስከመጨረሻው ሸኝቶ ወደ እህቱ ሲዞር የሰጠቻትን ብር እየቆጠረች ነበር፡፡በትዝብትና በገረሜታ ይከታተላት ጀመር፡፡
ጨረሰችና‹‹አዎ ትክክል ነች..ሶስት ሺ ብር ነው፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

05 Nov, 18:38


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-16
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

///
ኮሎምቢያ/አማዞን ደን ውስጥ
ኑሀሚና ካርሎስ አምስት ሰዓት ያለምንም ረፍትና መንቀርፈፍ ነው የተጓዙት፡፡በቀንም ቢሆን እንኳን ፀሀይ የተንጣለሉትን የግዙፍ ዛፎችን ቅርንጫፍ ሰንጥቃ ወደመሬት መድረስ አይሆንላትም፤ ማታ ሲሆን ደግሞ ለጨረቃዋ በጣም ከባድ ስራ ነው የሚሆንባት፡፡ በዚህም ምክንያት በማታ አይደለም በቀንም ከፍተኛ ሀይል ያለው ባትሪ ሳይጠቀሙ መጓዝ አዳጋች እና በቀላሉ ለአደጋ የሚያጋልጥ ስራ ነው፡፡
‹‹አሁን ማረፍ ያለብን ይመስለኛል››አላት ካርሎስ

‹‹ይሻላል ብለህ ነው?››አለችው በዛለና በደከመ ድምጽ፡፡

‹‹አዎ አሁን የተወሰነ የራቅናቸው ይምስለኛል…ባይሆነ ለሊቱን አርፈን ንጊት ላይ በሙሉ አቅም ጉዞችንን እንቀጥላለን፡፡››አላትና ተስማሙ፡፡ቅጠል እየቆረጠች ግዘፉ ግንድ ስር መጓዝጎዝ ጀመረች፡፡
‹‹ምን እየሰራሽ ነው?፡፡››

‹‹መሬት ላይ ከመቀመጥ ቅጠሉ ይሻለናል ብዬ ነዋ፡፡››

‹‹እዚህ የአማዞን እንብርት ላይ መሬት ላይ ተዝናተን መተኛት አንችልም…››

‹‹ለምን? ጃጓር ምናምን ፈርተህ ነው?››

‹‹እሱም አንድ ነገር ነው..ካዛ በላይ ግን ጥቃቅን መርዛማ ነፍሳቶች ናቸው የሚያስፈሩት…..ለምሳሌ የአማዞን ሸረሪት ሰውነትሽን ጥቂት ከጫረችሽ ወይ ከቦጨቀችሽ….በቀጥታ እራስሽን ለሞት ማዘጋጀት መጀመር ነው ያለብሽ፡፡በጣም ብርቱ ከሆንሽ አንድ ሰዓት ብቻ ነው የምትኖሪው፡፡መርዙን አርክሶ ከሞት የሚያድንሽ ምንም አይነት ባህላዊም ሆነ ዘመናዊ መድሀኒት የለም፡፡እና ይህችን ሸረሪት በቁጥር አንድ ደረጃ ነው የምፈራት፡፡››
ፍራቻው ወደእሷም ተጋባበትና‹‹እና ምን እናድርግ?፡፡››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹ሊያስተኛን የሚችል ዛፍ ነው መፈለግ ያለብን ..››ብሎ አይኖቹን በአካባቢው ወደሉት ግዙፍ ዛፎች ባትሪውና በማብራት መምረጥ ጀመረ…ከዛ ‹‹አዎ ይሄኛው የተሻለ ነው….፡፡››ስል ምራጫውን አሳወቃት፡፡
‹‹እንዴት አድርገን ነው እዚህ ላይ ምንወጣው?››

‹‹እንደምንም መውጣት ነዋ….መቼስ ቢከብድ ቢከብድ የሰው ህይወት ከማጥፋት በላይ አይከብድም፡፡››
በንግግሩ ድንግጥ አለች፡፡እስከአሁን እዛ ለእሷ በተቆፈረው መቃብር አካባቢ ስለሆነው ነገር አንሰተው አላወሩም‹‹ሰው መግደሉን ፈልጌው ወይም ቀላል ሆኖልኝ መሰለህ..?ጨንቆኝና የሞት ሽረት ጉዳይ ሆኖብኝ ነው፡፡››
‹‹እኮ እኔስ ምን አልኩ…?ይሄም የህይወት እና የሞት ትግል ነው፡፡ከዚህ ደን በአውሬ ሳንበላ ወይም በነፍሳት ሳንነደፉ በሰላም ወጥተን የሆነ መንግስት የሚቆጣጠረው ትንሽዬም ቢሆን ከተማ ወይም መንደር እስክንገባ የህይወትና የሞት ሽረት ላይ እንደሆን እንዳትዘነጊ…. በይ ቦርሳሽን ለእኔ ስጪኝና ለመውጣት ተዘጋጂ …እኔ ከኃላ ሆኜ እደግፍሻለሁ፡፡››
የተወሰነ ጊዜ እንደማሰብ አለችና ትከሻዋ ላይ ያንጠለጠለችውን ቦርሳ አቀበለችው፡፡ተቀበላትና ካንጠለጠለው ቦርሳ ጋር አንድ ላይ በቀኝ ትከሻው ደርቦ አንጠለጠለው፡፡በግራ ትከሻው ላይ ክላሽ አለ፡፡
እሷ በረጅሙ ትንፋሽ ወሰደችና ለመውጣት ዝግጁ ሆነች፡፡ቀኝ እግሯን አስቀደመች…ወገቧን ይዞ ደጋፋት፡፡ በእጆቿ ቅርብ ያለውን ቅርንጫፍ ተንጠራርታ ያዘችና ግራ እግሯን አስከተለች፡፡ እንዳዛ እያለች ወደ ላይ መንቀሳቀሷን ቀጠለች፡፡እሱ ከስር ሆኖ ትወድቅ ይሆን በሚል ስጋት በጭንቀት እየተከታተላት ነው፡፡እንደፈራው ሳይሆን እንደውም ይበልጥ አንድ ርምጃ ወደላይ ከፍ ባለች ቁጥር ይበልጥ እየፈጠነችና በራስ መተማመን እየታየባት መጣች፡፡ ለመተኛት ምቹ ነው ብሎ ያሰበበት ቦታ ስትደርስ ‹‹በቃሽ…እዛው ጠብቂኝ›› አላት፡፡እሱም በእፎይታ ወደላይ መውጣት ጀመረ፡፡እሱ ከልጅነቱ ጀምሮ የብዙ አመት ልምድ ስላለው ዛፍ መውጣት ለእሱ በምድር እንደመራመድ ቀላሉ እና ተራ ነገር ነው፡፡
ስሯ ደረሰና ከጎኗ ቁጭ ብሎ የእሷንም የእሱንም ቦርሳ ከአንደኛው ቅርንጫፍ ላይ አሰረው፡፡መሳሪያውንም እንደዛው አንጠለጠለውና በእፎይታ ደገፍ ብሎ ተቀመጠ፡፡ ካልተመቸሽ እግርሽን በቅረንጫፉ መሀከል አድርጊና ጭንቅላትሽን እኔ ላይ አስደግፊ አላት፡፡››እንዳለት አደረገች፡፡ጭንቅላቷን ደረቱ ላይ ለጥፋ አረፍ ስትል የልብ ምቱ ድውድውታ ተሰማት፡፡
‹‹ልብህ በጣም ይመታል፡፡›› አለችው፡፡

‹‹አንቺን የመሰለች ፀይም መልዐክ ደረቴ ላይ ተኝታ የልብ ምቴ ባይጨምር ነበር የሚገርመው››አላት፡፡
‹‹አይገርምም …የዛሬን አያድረገውና አለቃህም በሰላሙ ቀን ፀይም መልአክ ብሎኝ ነበር››

‹‹እንደዘ በማለቱ እንኳን ተሳስቷል ማለት አልችልም…የእሱም ልብ እንደእኔው በውበትሽ ደንዝዛ ነበር ማለት ነው፡፡››
‹‹በዚህ ጣር ላይ ሆነህ ትቀልዳለህ አይደል?››

‹‹በጣር ላይ ሆንሽ በምቾት ላይ ልብሽ ጉዳዩ አይደለም እኮ …ከተነካ ተነካ ነው..በሲኦሉ ውስጥም ሆነ በገነት እጅ መስጠቱ አይቀርም፡፡››
‹‹ይሁንልህ…ውሀው አለቀች እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡ውሀ ጠምቷት ብቻ ሳይሆን የጀመሩትን የወሬ ርዕስ አቅጣጫ ማስቀየርም ስለፈለገች ነው፡፡የእሱን ልብ አታውቅም የእሷ ልብ ግን በዚህ ጊዜ ነፍሷን ለወንድሟ ስትል ከማትረፍ ውጭ ሌላ ተልዕኮ የላትም፡፡እጁን ወደተንጠለጠለው ቦርሳ ሰደደና ኮዳውን አውጥቶ ሰጣት፡፡ክዳኑን ከፈተችና ተጎነጨችለት፡፡መልሳ ከድና አቀበለችው፡፡ወደቦታው መለሰ፡፡
‹‹አሁን የት ነው ያለነው?፡፡››ስትል ጠየቀችው፡፡

‹‹የአማዞን ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ነዋ፡፡››

‹‹እሱንእማ እያየሁት ነው…ሀገሩን ነው የጠየቅኩት፡፡
‹‹ብራዚል እና ኮሎምቢያ ድንበር ላይ ነን፡፡››
‹‹እንዴ …!ወደየት ነው እየሄድን ያለነው?››

‹‹ወደብራዚል ነው…››

‹‹ወደኮሎምቢያ ወይም ወደመጣንበት ወደፔሩ የምንሄድ ነበር የመሰለኝ፡፡››

‹‹አይ …ያንን ማድረግ አልመረጥኩም…ከፔሩ ፤ኮሎምቢያ ሜክሲኮ አልፎ አሜሪካ ድረስ ሰውዬው በብዙ ሺ የሚሆኑ ሰዎች አሉት…በየደረስንበት ሁለ ታዳኞች ነው የምንሆነው፡፡ይሄኔ ሁሉም እኛን በደረስንበት ቀጨም አድርጎ ወይ በህይወት ካለሆን ደግሞ እሬሳችንን ለእሱ በማስረከብ እና ደለብ ያለ ሽልማቱን ለመቀበል ቋምጠው እየጠበቁን ነው፡፡››
‹‹ብራዚልስ ሰው የለውም?››

‹‹አይ ብራዚል ተፅእኖው በጣም የሳሳ ነው፡፡በዛ ላይ አሁን እየተጓዝን ያለነው ወደግዙፍ ጥቅጥቅ የአማዞን ደን ነው..በቀደም እንደነገርኩሽ 60 ፐርሰንቱ የአማዞን ደን ያለው ብራዚል ውስጥ ነው፡፡ወደእዛ ጠልቀው ይገባሉ ብሎ ማንም አያስብም፡፡ገብተዋል ብለው ቢያስብ እንኳን ያን ሁሉ ደን ሰንጥቀን ከአውሬዎቹም ከተናዳፊ መራዛማ ነፍሳትም ተርፈን በህይወት የሆነ ቦታ እንደማንደርስ እርግጠኞች ናቸው..ስለዚህ ወደዚህ አይፈልጉንም፡፡ለዛ ነው በጣም ከባዱን መንገድ የመረጥኩት፡፡በህይወት እንዲሳካልሽ አንዳንዴ ቀላሉን መንገድ መምረጥ አዋጪ አይደለም…፡፡››
ፈገግ አለችና‹‹አሳምነኸኛል..ግን አንተስ ከፊታችን እንደፓስፊክ ውቅያኖስ የተዘረጋውን አስፈሪ ጥቅጥቅ ደን ሰርቫይቭ አድረገን ሕይወታችንን እንደምናተርፍ እንዴት ልታምን ቻልክ?፡፡››
‹‹በቀደም በነገርሺኝ ታሪክ ነዋ››

‹‹የትኛው ታሪክ?፡፡››

‹‹የሴትዬዋ… ጨካኝ ንጉስ ያለበት ግዛት ውስጥ ከመኖር አዳኝ ነበር ያለበት ጫካ ውስጥ መኖር እንደሚሻል መምረጦን የነገርሺኝን…››
በጨለማ ውስጥ ፈገግ ብላ‹‹ጥሩ ተማሪ ነህ፡፡››አለችው ፡፡

‹‹አዎ ጥሩ ተማሪ ነኝ..በዛ ላይ ሶስት ነገሮች ያግዙናል ብዬ አስባለው፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

03 Nov, 17:50


‹‹ጥያቄሽ ነው ያሳቀኝ …አንቺ እንድትገደይ ትዕዛዙን ያስተላለፈው ሀለቃችን አሁን አንቺ የምትጨነቂለት ዳግላስ መሆኑን ሳስብ ነው ያሳቀኝ..አየሽ አለም በእንደዚህ ይነት ገራሚ ምፀቶች የተሞላች ነች፡፡››
እርምጃውን ገታችና ባለችበት ቆመች..ከኃላ እየተከተላቸው ታጣቂ አይኑን አጉረጠረጠ…የጓደኛውም ሆነ የተገዳዮ ነገረ ስራ ምንም አላማረውም…ጣልቃ ላለመግባት ነው እንጂ ወሬያቸውም አልተመቸውም.. ምክንያቱም እሱ ስፓኒሽኛ ተናጋሪ ሲሆን እንሱ እያወሩ ያሉት በእንግሊዘኛ ነው..እሱ ደግ እንግሊዘኛ ጆሮውን ቢቆርጡጥ አይሰማም፡፡
‹‹ማለት ከእኔ ጋር ያገታችሁት በሌላ ጀልባ ወደሌላ ስፍራ የወሰዳችሁት ዳግላስ የእናንተ ሀለቃ ነው?››ማመን ስላልቻለች ደግማ ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እሱ የእኛ ብቻ ሳይሆን በሺ ሚቆጠሩ ሌሎች የታጣቂ ቡድኖች መሪ የጫካው ንጉስ እየተባለ   የሚጠራ   ከፍተኛ   ቢሊዬን   ዶላሮች   የሚያንቀሳቅስ   ከፔሩ፤ ኮሎምበያ፤ ፓናማ፤ ነካረጎ፤ ጉታማላ፤  ሚክሲኮ አልፎ አሜሪካ ድረስ እሱ የሚቆጣጠረው የንግድ መስመር ያለው በሶስት በአራት ሀገራት የደህንነት ሰዎች ሚፈለግ አለማ አቀፉ የኢንተርፖል የተፈላጊዎች ስም ዝርዝር ውስጥ የመጀመሪያው ገፅ ላይ የሰፈረ ተአምረኛ ሰው ነው፡፡››የሚላትና ማመን ነው እያቃታት፡፡‹‹እና እሱ እንደእዛ አይነት ሰው ከሆነ ለምን ከእኔ እኩል አፈናችሁት?፡፡››ስትል ጠየቀች፡፡
‹‹ሰውዬው መድሀኒቱን በጊዜ ካልወሰደ ከፍተኛ የመርሳት ችግር አለበት..ማለት እራሱንና ማንነቱን ሙሉ በሙሉ እስኪዘነጋ ድረስ ይደርሳል፡፡ከንቺ ጋር ሊማ አየር ማረፊያ ተገናኝታችሁ ኢኩቶስ እስክታርፉ ድረስ ከዛም ሆቴል ይዛችሁ ስታድሩ ሁሉ ያገጠማችሁ ያ ነው፡፡በወቅቱ ችግሩ እንደተፈጠረ ስናውቅ በግል ቻርተር አውሮፕላን እናንተ ወዳላችሁበት መጣን፡፡ ቀጥታ ሄደን ብናናግረው..አላውቃችሁም ሊለን ይችላል፡፡ ክርክር ብንገጥም ጭቅጭቅ ቢነሳ ደግሞ ትኩረት እንስባለን…እንዳልኩሽ በአለም አቀፍ ደረጀ የሚፈለግ ሰው ነው…ስለዚህ ሁኔታውን አመቻችተን ማፈን ነበረብን፡፡ለዛ ነው እንደዛ ያደረግነው፡፡››
‹‹ጥሩ እዚህ ሁሉ ውስጥ ታዲያ እኔ ምንድነው ያደረኩተት?፡፡››ስትል በአግሯሞት ጠየቀችው፡
‹‹ከእሱ ጋር አንድ ቀን አሳልፈሻል…. አንድ ቀን አብረሽው አድረሻል…ስለእሱ ምን መረጃ እንዳወቅሽ አይታወቅም…መጀመሪያውኑ ከእሱ ጋር ያንን ጊዜ ያሳለፍሽው ዝም ብለሽ በየዋህነት ነው..?በውበቱ ተማርከሽ ሴትነትሽን ልትሰጪው ነው..?ወይንስ የሆነ የደህንነት ተቋም ያሰማራሽ ሰላይ ነሽ…?ይሄ ነው ጥርጣሬችን››
‹‹ታዲያ ይሄንን የምታጣሩበት ዘዴ የላችሁም?፡፡››

‹‹አለን…እኔም እንደዛ እንደሚደረግ ነበር ተስፋ ያደረኩት…በተጨማሪም ከሰውዬው ጋር ባሳለፍሽው አንድ ቀን ጥሩ ጊዜ ካሳለፋችሁ ያንን ከግንዛቤ አስገብቶ የተሻለ ውሳኔ ይወስናል ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር..ግን ሁሉ ነገር ካሰብኩት በተቃራኒ ነው የሆነው…ለነገሩ ሰውዬው ሁሌ እንደዚህ ነው..የመግደል ሱስ አለበት፡፡››
ጓደኛው በስፓኒሽኛ ያወራው ጀመር ..ትንሽ ተጨቃጨቁና ተስማሙ፡፡

‹‹ምንድነው የሚለው?››

‹‹አይ ይበቃናል..በቃ የምትቀበርበትን ጉድጓድ ትቆፍር ነው የሚለው፡፡›› ዝም አለች፡፡
‹‹እዛ ድንጋይ ላይ ተቀመጪ››አላት..ዝም ብላው ሄደችና እንዳላት ተቀመጠች፡፡

ካርሎስ አካፋውን ከጓደኛው ተቀበለውና የመቆፈሪያውን ክፍል አስተካክሎ እራሱ መቆፈር ጀመረ..መሬቱን በሚቆፍርበት መጠን የገዛ ልቡም እየተቆፈረበት ነው፡፡‹‹አሁን የእውነት ይህቺን የመሰለች ልጅ ተኩሼ ገድላታለው?፡፡››እራሱን ይጠይቃል፡፡አይ እንደዛማ ማድረግ አልችልም፡፡ለራሱ ይመልሳል፡፡ግን ደግሞ ትዕዛዙን ተግባራዊ አለማድረግ ከለምንም ምህረት ምን እንደሚያስከትልበት በደንብ ያውቃል፡፡በቃ ሞት ነው..ለዛውም ለሌሎቹ መቀጣጫ በሚሆንበት መንገድ አሰቃቂ የሆነ ሞት ነው የሚጠብቀው፡፡
‹‹ለዚህች ለአራት ቀን ብቻ ለማውቃት ሴት ህልሜንም ህይወቴንም ልሰዋላት ዝግጁ ነኝ?››ሲል እራሱን ጠየቀ….መልሱ ቀላል እልሆነለትም፡፡
ጓደኛው ሊያግዘው ወደእሱ ተጠጋ፡፡ ከጉድጓዱ እንዲወጣ ጠየቀው ..መሳሪያውን ከትከሻው አነሳና አቀበለውና ወደጉድጓዱ ገባ…እየተፈራረቁ ጉድጓዱን ቆፍሮ ለማጠናቀቅ 30 ደቂቃ ያህል ፈጀባቸው፡፡ከዛ የመጨረሻውን ርምጃ ለመውሰድ ዝግጁ ሆኑ፡፡ አነሱም ለመግደል እሷም ለመሞት …ድንገት ወደ እሷ ሄደና ‹‹በጣም አዝናለሁ….ላድንሽ ባለመቻሌ በራሴ አፍሬለሁ››አለና ጉንጮን ስሞ ብድግ አለና ፊቱን አዞረ ፡፡
ካርሎስ ‹‹በቃ አንተ አድርገው…….እኔ ወደእዛ ዞር ብዬ ላጭስ››ብሎ ለጓደኛው ነገረውና ወደግራው ዞር ብሎ ሶስት ያህል  ርምጃ እንደተራመደ…ኑሀሚ ልክ እንደተናዳፊ ንብ ከተቀመጠችበት ተስፈነጠረችና የካርሎስን አንገት በእጆቾ ፈጥርቃ ይዛ በሌላ እጇ ወገቡ ላይ ያለውን ሽጉጥ መዘዘችና ግንባሩ ላይ ደቀነችበት‹‹አንተ ብቻ አይደለህም እኔም አንተን የመሰለ ቅን ፤መልካምና ፤ጀንትል ሰው ጋር የገዛ ህይወትን ለማትረፍ መፋለም በመገደዴ በጣም አዝናለው፡፡››አለችው
በዚህ ጊዜ ሁለተኛው ታጣቂ የያዘውን ዘመናዊ መሳሪያ በእሷ ትክክል ደቅኖ በማይገባት ቋንቋ ይለፈልፋ ጀመር፡፡
‹‹አይ አትዘኚ….ምን አለ በራሷ ተነሳሽነት የሆነ ነገር ማድረግ በቻለች እያልኩ ስፀልይ ነበር….የቻልሺውን አድርጊ ..በፀጋ እቀበላለው፡››አላት
‹‹እሺ ጓደኛህ መሳሪያውን እንዲያስቀምጥ ንገረው፡፡››

እንዳለችው በሚገባው የስፓኒሽ ቋንቋ ነገረው፡፡መለሰለት፡፡

‹‹ምን አለ?››ጠየቀችው፡፡

‹‹በተአምር የሀለቃዬን ትዕዛዝ እንዲከሽፍ ማድረግ አልችልም….››ነው ሚለው፡፡

‹‹እንዴ ….ካለስቀመጠ እኮ ተኩስብሀለው..ይሄንን አልነገርከውም?››

‹‹ነግሬዋለው..እሱም ገብቶታል፡፡ ግን እንደእሱ ውሳኔ እኔን ለማትረፍ በመጣር ነገሩን ከማበላሸት እኔን መስዋእት ማድረግን መርጧል፡፡››
‹‹እንደዛ የሚያደርግ ይመስልሀል?››

‹‹እንደአለመታደል ሆኖ ይመስለኛል….አንድም ቀን በመሀለከላችን መግባት ኖሮ አያውቅም….እንደዚህ አይነት አጋጣሚዎችን ለአመታት ሲጠብቅ እንደነበረ ነው የሚገባኝ፡፡››
እንግዲያው….አለችን በብርሀን ፍጥነት ሽጉጦን ከእሱ ግንባር አንስታ አቅጣጫውን ቀየረችና ተኮሰች …ደገመችው…ሰውዬው በቆመበት አይኑ እንዳፈጠጠ ተመለከታት..ከመሀል ግንባሩ ደም ቡልቅ ቡልቅ እያለ መውረድ ጀመረ ..ወዲያው ሽብርክ ብሎ ወደፊት ተደፋ፡፡ከዛ ለቀቀችውና ፈንጠር ብላ ቆመች፡፡
አንዴ መሬት ላይ ተዘርሮ በደም የታጠበው ጓደኛውን አንዴ እሷን እያፈራረቀ እያየ ግራ በመጋባት ደቂቃዎች አሳለፈ….ከዛ በርከክ ብሎ ጓደኛውን ገለበጠው…እጁን ወደ አንገቱ ልኮ በህይወት መኖር አለመኖሩን ተመለከተ፡፡
ሞቷል፡፡ኪሱን ፈተሸና የያዛቸውን እቃዎች አወጣ፡፡ እየጎተተ ለኑሀሚ ወደተቆፈረው ጉድጓድ ወሰደውና ውስጥ ከተተው፡፡ከዛ በአካፋው አፈሩን መለሰና ደለደለው..ካዛ አዲስ የተቆፈረ መሆኑን እንዳያስታውቅ የደራረቁ ቅጠሎችና እንጨቶችን ከአካባቢው እየሰበሰበ አለበሰባትና በተቻላ መጠን ከአካባቢው መሬት ጋር በእይታ እንዲመሳሰል አደረገ፡፡መሳሪያውን ታጠቀ…ከኪሱ ያወጣቸውን እቃዎች የገዛ ኪሱ ውስጥ ጨመረ.. .ሟቹ ጓደኛ ይዞት የነበረውን የእሷን ቦርሳ አቀበላትና ….ከዛ ጎደኛው ጀርባ ላይ ከነበረው የመንገድ ሻንጣ ጠቃሚ ነው ያላቸውን እቃዎች…ባትሪ ከነተለዋጭ ድንጋዩ፤የተወሰኑ የታሸጉ ምግቦችን፤ሲቆፍሩበት ያነበረውን አካፋ መርጦ ወደረሱ ቦርሳ በመጨመር ‹‹በይ ፈጠን በይ እንሂድ›› አለትና ወደፊት መጓዝ ጀመረ፡፡
‹‹ወደየት ነው የምንሄደው?፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

03 Nov, 17:49


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-14
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

‹‹ይሄ መንገድ ግን ወደ መጣንበት አቅጣጫ የሚወስድ አይደል እንዴ?››በጥርጣሬ ጠየቀች፡፡
‹‹አይ አይደለም…..ትንሽ ከተጓዝን በኃላ እንታጠፋለን፡፡››ሲል ድጋሜ ዋሻት፡፡

ከዛ በኃላ ለ10 ደቂቃ ያህል ጫካውን ቁጥቆጦ እየገፉና እሾክና እንቅፋቶችን ከፊታቸው እያስወገድ ወደፊት ከመጓዝ ውጭ በሶስቱም መካከል ምንም ንግግር አልነበረም፡፡
ኑሀሚ የህይወቷ የመጨረሻ ጫፍ ላይ እንደደረሰች ተስምቷታል፡፡ከቡድኑ ነጥለው ወደጫካው እየነዷት ያለው ለሰላም እንዳልሆነ ወዲያው ነው የገባት፡፡ በተለይ የካርሎስ መርበትበትና በፊቱ ላይ እየተመለከተችው ያለው ሀዘን በጥርጣሬዋ እርግጠኛ እንደትሆን አድርጓታል፡፡ በዛ ላይ ከኃላ ሆኗ የሚከተላቸው ፊቱ የማፈታው ታጣቂ በጀርባው ባነገተው ቦርሳ አካፋም መቆፈሪያም ሆኖ የሚያገለግል ወታደሮች ምሽግ ለመስራት የሚጠቀሙበትን መሳሪያ ይዞ በማየቷ ሌላ እርግጠኛ እንድትሆን ያደረጋት ምልክት ነው፡፡
አካባቢን ማጥናት..ማንኛውንም እንቅስቃሴ በንቃት መከታተል..ከዛ የይሆናል ትንበያዎችን አስቀምጦ ከቅርቃሩ ለመውጣት የሚያስችሉ አማራጮችን በፍጥነት ማስላት….በስለላ ህይወቷ የቀሰመችው ትምህርት ነው፡፡
እና ዝም ብላ መሞት እንደሌለባት እራሷን እያሳመነች ነው፡፡በህይወቷ እንዲህ መሰል በህይወትና በሞት ቅርቃር መካከል የመውደቅን አጋጣሚ ብዙ ጊዜ ገጥሞት ያውቃል፡፡ በአምስት ሰዎች ተከባ ልትገደል ብላ ግማሹን ገንድሳ ግማሹን ገድላ ነፃ የወጣችበትና ህይወቷን ያተረፈችበት አጋጣሚ ነበረ፡፡ከእዛ አንጻር ሲታይ ይሄ ቀላል ይመስላል..ምክንያቱም ከሁለት ታጣቂዎች ጋር ነው የምትፋለመው፡፡ ካላት ወታደራዊ እውቀትና ልምድ አንፃር አነሱን ገድላ ወይ ፌንት አስበልታ የማምለጥ እድሏ ከ50 ፐርሰንት በላይ ነው ፡፡..ችግሩ ካመለጠች በኃላ ነው፡፡ፊቷ ያፈጠጠው ምኑንም የማታውቀው በየት ገብታ በየት መውጣት እንዳለባት ምንም እውቀት የሌላት የአማዞን ጫካ ነው፡፡ጫካ ውስጥ ያሉት አስፈሪና በስም እንኳን ለይታ የማታውቃቸው አውሬዎችና አንድ ጠብታ መርዛቸው እንኳን ሰውነት ላይ ሲያርፍ በሰከንድ ውስጥ የሚያደርቅ ተሳቢ እንስሳትና በራሪ ነፍሳት ጋር ነው፡፡ቢሆን በሰው ተቦጫጭቆ ከመበላት በአውሬ ጋር ለመፋለም ቁርጠኛ መሆን ይሻላል
፡፡በዚህ ቅፅበት አንድ ታሪክ ትዝ አላትና ለካርሎስ ልትተርክለት ፈለገች፡፡

‹‹አንድ ጣፍጭ ታርክ ልንገርህ?››

እንደ እሱ ግንዛቤ ሰዓቱ ታሪክ መንገሪያም ሆና ማዳመጪያ እንዳልሆነ ቢያምንም ለእሷ ግን ምን አልባት የመጨረሻ ቃሏ ሊሆንላት ይችላል ብሎ ስላሰበ እንድትነግረው ተስማማ፡፡
‹‹ጨቋኝ ገዢ ወይም የሰው ልጅ  ከገዳይ ነብር የበለጠ አስፈሪ እንደሆነ የሚያስረዳ ታሪክ ነው፡፡
‹‹ገባኝ ንገሪኝ…››

ከአንድ የድሮ መፅሀፍ ላይ ያነበብኩት ታሪክ ነው፡፡በአንድ ወቅት በቻይና ግዛት ውስጥ በምትገኘው በታይ ተራራ ስር በሀዘን ተቆራምዳ እንባዋን እያዘራች የምትኖር ሴት ነበረች፡፡የዚህችን ሴት ታሪክ ኮንፌሽዬስ ሰማና አስጠራት፡፡ከዛም"አንቺ ሴት ምን ሆነሽ ነው እንዲህ ሀዘን የበላሽ?"ሲል ጠየቃት።ሴቲቱም ‹‹በተራራው ላይ የሚኖረው ነብር ባሌን ፣የባሌን አባት እና ብቸኛ ልጄን በየተራ እየቀረጣጠፈ በላብኝ-በዛ ምክንያት ነው ሀዘኔ ጥልቅ የሆነው›› ብላ መለሰችለት።
እሱም መልሶ "ታዲያ መላ ቤተሠቦችሽን የበላው ነብር አሁንም በተራራው ላይ መኖን እያወቅሽ .እንዴት ከአካባቢው ሳትሸሺ?››ሲል በመገረም ጠየቃት።
ሴቲቱም‹‹ቦታውን ለቅቄ ያልተሠደድኩት ጨካኝ ገዢ የሌለበት ብቸኛ  ስፍራ ስለሆነ ነው።"ስትል መለሠችለት
ኮንፌሽዬስም ወደ ደቀመዛሙርቱ ዞሮ" አያችሁ ጨቋኝ ገዢ ከገዳይ ነብር የበለጠ አስፈሪ እንደሆነ ከዚህች ሚስኪን ሴት ታሪክ ተማሩ፡፡›› አላቸው።
እኔም አሁን እዚህ አማዞን ደን ውስጥ ካሉት አውሬዎች በላይ ጨካኝ የሆኑ የሰው ልጆች ናቸው እያሰፈሩኝ ያሉት››ብላ ታሪኩን ደመደመች፡፡
‹‹አልተሳሳትሽም….የሰው ልጅ መጨከን ከጀመረ ወሰኑ አይደረስበትም…››

‹‹እኔ ምልህ ..አሁን ልትገድሉኝ ነው አይደል?››

ጥያቄዋ አስደነገጠው…ምን ብሎ እንደሚመልስላት ግራ ስለገባው…ዝም አለ…‹‹አትጨነቅ..ግን ያልገባኝ እንዲህ ልትገድሉኝ ይሄን ሁሉ ቀን እኔንም ማንከራተት እናንተም ከእኔ ጋር መንከራተት ለምን አስፈለገ?››
‹‹ትዕዛዙ የደረሰን አሁን ነው…››

‹‹ትዕዛዙን የሚሰጠው ማን ነው››

‹‹ሀለቃችን ነው…ካለበት ቦታ በሳተላይት መገናኛ ነው ከደቂቃዎች በፊት ትገደል ያለው፡፡››

‹‹ይገርማል…ቆይ ግን ከእኔ ጋር ያገኛችሁትን ሰውዬ ገድላችሁታል አይደል?››

ፈገግ አለ፡፡

የፊቱን ፈገግታ በቆረጣ እይታ አየችውና ተበሳጨችበት…‹‹ምነው? የሰው መገደል ያስቃል እንዴ?››
‹‹አረ በፍፅም … እንደውም በተቃራኒው ልቤን ነው የሚሰባብረው፡፡››

‹‹አይ ስትስቅ አየሁህ ብዬ ነው፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

03 Nov, 13:10


🇪🇹በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አበይት ክንውኖች  🇪🇹

✏️ሚያዝያ  28/1875  አፄ ምንሊክ ከ እቴጌዪቱ ተጋቡ።

✏️ሚያዝያ 25/1881 ምንሊክ ከጣሊያን ጋር ውጫሌ ውል ተፈራረሙ።

✏️ ጥቅምት 2/1888 ለአድዋ ዘመቻ ምንሊክ  ከአዲስአበባ ተነሱ።

✏️ሕዳር  28/1888 አምባላጌ ጦርነት ላይ ኢጣልያኖች ተሸንፈው ሸሹ።

✏️ ታህሳስ 28/1888 ራስ መኮንን የመቀሌን ምሽግ ከኢጣልያን አስለቀቁ።

✏️ የካቲት 23/1888  አድዋ

✏️ጥቅምት 20/1902 የልጅ ኢያሱ  ወራሽነት እንዲሁም የራስ ተሰማ ናደው ሞግዚትነት  አፄ ምንሊክ አሳወጁ።

✏️መጋቢት 12/1902  እቴጌ ጣይቱ ከፖለቲካ ስልጣናቸው እንዲለቁ ተወሰነ።

✏️ታህሳስ 3/1906 አፄ ምንሊክ አረፉ በምትካቸውም ልጅ ኢያሱ  ነገሡ።


🔎 የተጠቀሱት ዘመናት በኢትዮጵያውያን አቆጣጠር  መሆናቸውን ላሳስብ እወዳለሁ።


ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !!

ከመጽሐፍት መንደር💠

31 Oct, 18:48


ሚስት ምርጫ ሳትሆን ስጦታ ናት! ባልም እንዲሁ

አንድ ቀን አንድ የስነ-ልቦና መምህር ወደ ክፍል ገብቶ ተማሪዎቹን "ዛሬ ጌም ብንጫወት ምን ይመስላችኋል አላቸው?"

ምን አይነት ጌም እንደሆነ ሲጠይቁት፣ እሱን አብረን እናየዋለን አለና ከመካከላችሁ አንድ ፈቃደኛ ተማሪ እፈልጋለሁ አለ። አንድ ተማሪ እጅ አወጣና ጌሙ ተጀመረ።

መምህር:- "ሰላሳ በህይወትህ የምትወዳቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ፃፍ!" አለው።

ተማሪው:- ከቤተሰቦቹም፣ ከሩቅ ዘመዶቹም፣ ከጓደኞቹም እያለ የሰላሳ ሰው ስም ፃፈ።

መምህር:- "አሁን ከፃፍካቸው ውስጥ ብታጣቸው ግድ የማይሰጥህን አምስት ሰዎችን ስም ሰርዝ" አለው።

ተማሪውም አምስት ስም ሰረዘ ሰረዘ።
መምህሩ:- "አሁን ደግሞ የአስር ሰዎችን ስም ሰርዝ አለው"።

እንዲህ እንዲህ እያለ የአራት ሰዎች ስም ቀረው(የእናቱ፣ የአባቱ፣ የልጁና የሚስቱ)
መምህር:- "ከነዚህ ከ4ቱ ሰዎች ሁለቱን ሰርዝ አለው።"

ተማሪው: በከፍተኛ የሀዘን ስሜት ተውጦ የወላጆቹን ስም ሰረዘ።

መምህር:- "አሁን የቀሩህ ሁለት ሰዎች ሚስትህና ልጅህ ናቸው ከሁለቱ አንዱን አስቀርተህ አንደኛቸውን ሰርዝ አለው።"

ተማሪ:- በሃዘን እያነባ የልጁን ስም ሰረዘ። ተማሪዎቹ በሁኔታው ግራ ተጋብተው መጨረሻውን ለማወቅ ጓጉተዋል።

መምህር:- "ሚስትህ ብትሞት ሌላ ሚስት ማግባት ትችላለህ፣ እንዴት ከወላጆችህና ከልጅህ አብልጠህ ሚስትህን መረጥካት?" ሲል ጠየቀው።

ተማሪውም:- "ወላጆቼን አጥብቄ ብወዳቸውም እድሜያቸው ገፍቷልና በሞት ትተውኝ ይለዩኛል። ልጄም በፍቅር ተንሰፍስፌ ባሳድገውም ሲያድግ ጥሎኝ ወደሚስቱ ይሄዳል። በህይወት እስካለሁ ድረስ መቸም ቢሆን የማትለየኝ ሚስቴ ናት። ሚስቴ የኔ የምርጫ ጉዳይ ሳትሆን ስጦታዬ ናትና ለዛ ነው እሷን ያልሰረዝኩት" ብሎ መለሰ።

አብረውት የሚማሩት ተማሪዎች በመልሱ ተደስተው አጨበጨቡለት። መምህሩም አብሮ አጨበጨበለት! እኔም ታሪኩን ስሰማ እጀን ከፍ አድርጌ አጨበጨብኩለት!

ከመጽሐፍት መንደር💠

31 Oct, 17:18


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-13
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

///
ፔሩ/አማዞን ወንዝ ላይ
ዳግላስ ሚስቱ የሰጠችውን መድሀኒት ወስዶ ከተኛ ከሁለት ሰዓት በኃላ ነቃ፡፡አይኑን ሲገልጥ የቅንጡ ጀልባዋ መኝታ ቤት ውስጥ ብቻዋን ነው ያለው፡፡ ከነቃም በኃላ አይኑን ብቻ ገልጦ ዙሪያ ገባውን እየቃኘ ባለበት ሆኖ 15 ደቂቃ አሳለፈ፡፡፡ከዛ ተነሳና በራፉን ከፍቶ ‹‹ማሪያ…ማሪያ እያ ተጣራ››ስሙ ሳያስበው ነው አፉ ውስጥ የገባለት፡፡ ሚስቱ ተንደርድራ መጣችን ፊቱ ቆመች፡፡ ወደራሱ ጎትቶ አቀፋትና ደረቱ ላይ ለጥፎ ከንፈሯን ለረጅም ደቂቃ መጠጣት፡፡እሷም እጆቾን ዘርግታ በአንገቷ ዙሪያ አሽከርክራ አቀፈችውና እላዩ ላይ ተንጠለጠለችበት፡፡
‹‹ማሪያ የእኔ ውድ ..አንጀሊናስ?››
‹‹ከእነ ሳንዲያጎ ጋር ነች፡፡እጇን ይዞ እየጎተተ ወደጀልባዋ በረንዳ ወጣ፡፡ሲደርስ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ አስፈሪ ጠባቂዎች ከየተቀመጡበት በድንጋጤ ተነሱና ቀጥ ብለው ቆሙ….አንጀሊና አባቷን ስታይ ወደእሱ ተንደረደረች…በአየር ላይ ቀለባትና ግራና ቀኝ ክንዶን ይዞ አሽከረከራት፡፡ መርከቡ ላይ ያሉት ሁሉ ደስ አላቸው፡፡አሁን እራሱን ዳግላስን ሆኖል ማለት ነው፡፡ከልጁ ና ከሚስቱ ጋር ሀያ ለሚሆኑ ደቂቃዎች በማሳለፍ በመጠኑ ናፍቆቱን ከተወጣ በኃላ እነሱን ወደውስጥ ገብተው እንዲጠብቁት አዞ …ቀጥታ መርከቡ ላይ ካሉት 5 ታጣቂዎች ጋር ስብሰባ ተቀመጠ፡፡
‹‹እሺ እየሰማዋችሁ ነው፡፡››
የታጣቂዎች ሀለቃ የሚመስለው ግዝፍ ሰው አንገቱን እንደደፋ መናገር ጀመረ‹‹ሀለቃ በተፈጠረው ነገር በጣም እናዝናለን፡፡በእውነቱ ችግሩ እንደተፈጠረ ስንሰማ ወዲያው ነበር እርምጃ የወሰድነው››
‹‹እኮ ምን አደረጋችሁ?››
‹‹ያው ብራዚሊያ አየር ማረፊያ ገብታችሁ ነበር… አንተ ወደፕሌኑ ማለፍ ብትችልም አብሮህ የነበረው ፓብሎ ግን በፖሊስ እጅ ወደቀ፡፡አንተን ማሳለፍ ቢችልም እሱ እራሱን ግን ከፖሊሶች እጅ ማስመለጥ አልቻለም፡፡እና ምንም ልንረዳው ባለመቻላችን…ጠበቀ ያለ ምርመራ ሲደረግበት ስለአንተ የሆነ ሚስጥር ሊያወጣ ይችላል ብለን ስለሰጋን እዛው የገባበት እስር ቤት እርምጃ እንዲወሰድበት አድርገናል፡፡
አንተን ወደ ብራዚሊያ ይዛ የሚበረው አውሮፕላን በአየር ፀባይ ምክንያት ኢኩዩቶስ እንደረፈ ስንሰማ እኔ እራሴ ነኝ አንድ ቡድን እየመራሁ በቻርተር አውሮፕላን ወደዛ ያመራሁት፡፡ከዛ ምን አልባት የመንግስት ሰዎች ሆኑ የሲ.አይ.ኤ ሰዎች እጅ እንዳትገባ ተጠንቅቀን ከሆቴል ስትወጣ አፈነንህ ከኢኩዬቶስ አስወጣንህ፡፡
‹‹ጥሩ ስራ ነው….እርግጠኛ ነኝ ምንም ያዝረከረካችሁት ነገር የለም፡፡››
‹‹አረ የለም..ሁሉን ነገር በጥንቃቄ ነው የተከወነው…ግን….››
‹‹‹ግን ምን?››
‹‹አንድ የአንተን ውሳኔ የሚጠብቅ ጉዳይ አለን፡፡››

‹‹ምንድ ነው?››
‹‹ልጅቷን ምን እናድረጋት …?ምን አልባት የምትለው ነገር ይኖራል ብለን..ወደ ዋናው ሳንቺዋሪ እየወሰድናት ነው፡፡አሁን ላቲሲያ ደርሰዋል፡፡ለሁለት ቀን እዛ ቆይተው…ወደሳንቹዋሪ ይዘዋት ይመጣሉ፡፡
‹‹ምንድነው የምታወራው ..?የቷ ልጅ?››
ሰውዬው አንዴ ዳግላስን አንዴ ደግሞ ወደመርከቡ የውስጠኛ በራፍ እያየ ለመናገር ጊዜ ወሰደ‹‹እየጠየቅኩህ እኮ ነው..የምን ልጅ?››
ድምፁን ቀነሰና …‹‹ሆቴል ስናገኝህ ከሆነች አፍሪካዊት ልጅ ጋር ነበርክ….፡፡ ከኤርፖርት አብራችሁ ወጥታችሁ ሆቴልም አንድ ክፍል ነው ያደራችሁት፡፡››ለምን ድምፁ ቀንሶ እንደሚያወራ አሁን ገባው፡፡ከሴት ጋር አንድ ክፍል ውስጥ ማደሩን ሚስቱ ሰምታ ግርግር እንዳትፈጥር ነው፡፡አሱ ግን ያ ብዙ አላስጨነቀውም፡፡
‹‹እርግጠኛ ነህ..እንደዛ አድርጌለሁ?››
‹‹አዎ እርግጠኛ ነኝ…ምን አልባት ስለአንተ ማንነት ያወቀችው ነገር ይኖር ይሆናል ብለን ስለሰጋን ልንለቃት አልፈለግንም፡፡››
‹‹እና አሁን ወደሴንቸዋሪ ከሚጓዘው ቡዱን ጋር እየወሰድናት ነው እያልከኝ ነው፡፡››
‹‹አዎ፡፡››
‹‹ሽጉጥህን ስጠኝ ፡፡››ኮሰተር ያለ ትዕዛዝ አስተላለፈ፡፡ሁሉም በያለበት ሽምቅቅ አሉ፡፡ዳግላስ ሽጉጥ ስጠኝ ካለ የሆነ ችግር ሊፈጠር እንደሆነ ሁሉም ያውቃሉ፡፡ሽጉጥ እጁ ከገባ ይተኩሳል፡፡ሲተኩስ ደግሞ አየር ላይ አይደለም..ወይ አንዱ ደረት ላይ ወይ ደግሞ ጭንቅላት ላይ ነው የሚያሳርፈው፡፡በሚንቀጠቀጡ እጆቹ ሽጉጡን ከጎኑ መዞ ሰጠው…ግንባሩ ላይ ደቀነበት፡፡
‹‹እንዴት አንድ ምንነቷን የማታውቃትን መንገደኛ ሴት እየነዱ ወደግዛቴ ይዘዋት እንዲመጡ ትዕዛዝ ታስተላልፋለህ….?ምን ተልዕኮ እንዳላት ታውቃለህ…?ማን እንዳሰማራትስ?››
‹‹ጌታዬ ከፍተኛ ጥንቃቄ አድርገናል…ሙሉ እቃዋን ሆነ ጠቅላላ ሰውነቷን አብጠርጥረን ፈትሸናል፡፡ አታስፈልግም ካልከን አሁን ባለችበት እንዲያስወግዶት ማድረግ እችላለሁ፡፡››በፍርሀት በራደና በሚንቀጠቀት ድምፅ ሊያስረዳው ሞከረ፡፡
‹‹አይ መጀመሪያ አንተን አስወግድህና ትዕዛዙን እራሴ አስተላላፋለሁ፡፡››የሽጉጡን መጠበቂያ አላቀቀ….እጠቱን ምላጩ ላይ አሳረፈ…በዚህ ቅፅበት ልጁ‹‹አባዬ…አባዬ›› እያለች የጀልባውን በራፉ ከፍታ ወደእሱ ተንደረደረች….ቶሎ ብሎ የደቀነውን ሽጉጥ ከሰውዬው ግንባር ላይ አላቀቀና ጠረጴዛ ላይ ወርውሮ ከተቀመጠበት በመነሳት ወደ ልጅ ተንደረደረ፡፡አቃፋትና አባበላት፡፡ዝም ስትል ወደ ታጣቂዎች ዞረና ትዕዛዙን አሰስተላለፈ‹‹ በሉ አሁን ጉዞ እንቀጥል፡፡ እስከአሁን ያባከነው ሰዓት ይበቃል ፡፡ዛሬ ካምፕ ገብተን ማደር አለብን፡፡››
‹‹እሺ ጌታዬ ..ልጅቷን በተመለከተ ትዛዙን ላስተላልፍ?፡፡››
እንደማሰብ አለና‹‹..አይ ያንን ዕድልማ አጥተኸዋል…አሁን እራሴ የሚሆነውን አደርጋለው፡፡››ብሎ ወደውስጥ ገባ…..ጀልባዋም ተንቀሳቀሰችና ጉዞ ጀመረች፡፡
ወዲያው ነበር እጃቸው ላይ ያለችውን ሴት ገድለው ማንም እንዳያገኛት አድርገው እንዲቀብሯት ላቲሲያ ለሚገኙት ገዳዬቹ ትዕዛዝ የስተላለፈው፡፡
ኮለምቢያ
/ላቲሲ(አማዞን ወንዝን ታካ የተመሰረተች በአሳ ምርቶ የምትጣወቅ ከተማ) ካርሎስ ከገዳይ አጋሮቹ ፈንጠር ብሎ አንድ ግዙፍ ዛፍ ስር ቁጭ ብሎ በማስታወሻ ደብተሩ ላይ የቀን ውሎውንና ገጠመኞቹን በምጥን ቃላት እያሰፈረ ሳለ በቡድኑ ሀለቃ ተጠራ፡፡ማስተወሻ ደብተሩን አጣጥፎ ጎኑ ያለው የጉዞ ቦርሳው ውስጥ ከተተና መሳሪያውን በአንድ ተከሻው አንጠልጥሎ ቦርሳውን በእጁ ይዞ ወደተጠራበት ቦታ ሄደ፡፡
ቀጥታ ‹‹ግባና ግደላት፡፡››የሚል ትዕዛዝ ነበር የሰጠው፡፡

‹‹ምን ?››ካርሎስ ሀላቀውን በድንጋጤ ጠየቀ፡፡

‹‹ትልቁ ሀለቃችን ትገደል ብሏል…ግባና ግደላት፡፡››ኮስተር ብሎ በድጋሚ ትዕዛዙን አስተላለፈ፡፡
‹‹እርግጠኛ ናችሁ ትገደል ብሏል?››

‹‹ሰውዬ ያምሀል እንዴ? እኔ የተሳሳተ ትዕዛዝ ሳስተላልፈ አይተሀኝ ታቃለህ..?ነው ወይስ ፈራህ?ከፈራህ ግድ የለም ሌላ ሰው በደስታ ያድርገዋል፡፡እኔ እኮ ስለምትወዳት በፍቅር እንድትገድላት እድሉን ልስጥህ ብዬ ነው እንጂ ሌሎች በደስታ የሚፈፅሙት ትዕዛዝ መሆኑን አጥቼው አይደለም …ምንም ቢሆን እሷን እዚህ ድረስ በማጓጓዙ ከአንተ እኩል የለፋ የለም፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

30 Oct, 18:43


የኖትኮይን መስራች የሆነው #ሳሻ እና #የብሉም ምክትል Ceo ቭላድሚር ይሄ አዲሱን Paws ኤርድሮፕ ከጀመሩ ታዋቂ ሰዎች መካከል ይገኙበታል 😮‍💨🔥

Paws በብሉም በኦፊሺያል የትዊተር ገፅም በተደጋጋሚ የተተዋወቀ ሲሆን በWeb 3 የትዊተር ገፅም አዲሱ ዶግስ ይሆናል ሲሉ Paws ን ለብዙዎች አስተዋውቀዋል

Paws ላይ ያስገረሙኝ ነገሮች

1. ከቴሌግራም ድጋፍ ያለው መሆኑ
2. ከቴሌግራም ካልተደገፈ ቴሌግራም አካውንታችን የተጠቀምንበትን ቀን ማወቅ አስቸጋሪ ነው
2. ኖትኮይን የሰጠንን ቶክን ማወቁ
3. ዶግስ የሰጠንን ቶክን ማወቁ

እነዚህ ማሳያዎች የ Paws መስራቾች የሚታወቁ እና
#ከዶግስ #ከኖትኮይን እና #ብሉም በተጨማሪም #ከዱሮቭ ቴሌግራም ጋር ግንኙነት ያላቸው ሰዎች መሆናቸውን በቂ ማሳያ ነው

መጀመር ለምትፈልጉ ጊዜው ሳይሄድ በትጀምሩት አሪፍ ይመስለኛል 🫡

Link 👉
https://t.me/PAWSOG_bot/PAWS?startapp=NUvNTQ3l
https://t.me/PAWSOG_bot/PAWS?startapp=NUvNTQ3l

ከመጽሐፍት መንደር💠

29 Oct, 17:23


ነጋብኝ ለ'ኔ

ነጋልህ ደግሞ ቀኔን ልተነጥቀው
የዛሬውንም እለት ልትቆጣጠረው
እኔ እንደፈረደብኝ ላንተ እንዳደለህ
ንገስ በቀልቤ ላይ እንደ ራስ ግዛትህ

አንተ የማሰቢያዬ ብቸኛ ገዳይ
እኔ ደካማ ፍጡር
ሌላ ትርፍ ሀሳብ እንደሌለኝ ነገር
ራሴን የሚያዞር የኑሮ ስንክሳር
በሁሉም ደቂቃ በሰከንዱ ቁጥር
የተቆጠጠርከው ማሰቢያ ናላዬን
ሌላ እንዳላስብ እንዳልኖር ኑሮዬን
ሌላውን ፍጥረት ሁሉ ችላ አስብለኸኝ
በቃ አንተን ብቻ እንዳስብ አረከኝ
አንተ ክፉ ጨካኝ

ደግሞ እኮ አታፍርም እውድሻለሁ ስትል
ልቤ አታሞ ስትደልቅ ስትውል
በሌለህበት ድምፅህ በጆሮዬ ሲያቃጭል
የማልወጣበት ማጥ ውስጥ ጥለኸኝ
ለኔ ምን ሊረባኝ እውድሻለው ብትለኝ
አንተ ክፉ ጨካኝ

አስኪ ልጠይቅህ ቆይማ ስማኝ
ፍቅር ለምንደነው ነፍስ የሚሰቅዘው
አላላውስ ብሎ ፈገግታ ሚነጥቀው
አንተን አንተን ብቻ አንተን ብቻ የሚለው

ቆይ እኔ ምለው
ማስደሰት አልነበረ የመውደድ አላማው
ምቾት እና እረፍት ሰዉ እንዲሰማው
ታዲያ የኛ ብቻ ተለየብን ምነው
ሰላማችንን መንሳት ሆነ እኮ ስራችን
በጎ ምክንያት ሳይሆን ሆንን መጠፋፊያችን



ናኒ እንደገጠመችው

ከመጽሐፍት መንደር💠

28 Oct, 10:13


ን አልባት እኛ ያለን የሆነ ሰው ህልሙ ነው!
ምን አልባት እኛ ያለን የሆነ ሰው ፀሎቱ ነው !
ምን አልባት እኛ ያለፈን የማይጠቅመን ነው!
ምን አልባት ያሳመመን ሊያስተምረን ነው!
ምን አልባት የሆንነው የሆኑትን እንድንረዳ ነው !
ምን አልባት የተበለሻሸው እንድንቀያይረው ነው!
ምን አልባት አማራጭ ያጣነው አማራጭ እንድናመጣ ነው !

ከመጽሐፍት መንደር💠

27 Oct, 16:42


እናንተስ አጫውቱን እስቲ በምድር ላይ የትኛውን ገጠመኛችሁን ትወዱታላችሁ ???????

ከመጽሐፍት መንደር💠

27 Oct, 13:11


ጠላ እየጠጣን ከጓደኞቼ ጋ ተሰባስበን እየቀደድን ሳለ ፦

ምድር ላይ የትኛውን ገጠመኝህን በይበልጥ ትወዳዋለህ የሚል ቀደዳ ጀመርን

ፍሬንድ ቀጠለ

"አንድ እለት እሁድ ጠዋት እናቴ ቡና እየጠጣች ፣ እየመከረችኝ ፣ እየመረቀችኝ ፣ እየሰደበችኝ ሳለ

በጣምምም ደስስ የሚልሽ ምን ብታገኝ ነው አልኳት አጠያየቄ ድንገት ነበር

ላሊበላ ፣ አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ብሄድ ደስ ይለኛል አለቺኝ

ፊቷ ላይ ያለው ምኞት የደስታ ዳር ይመስል ነበር። ። በነጋታው ስጣደፍ ሄጄ ቢሮ አንድ መቶ ሺ ብር ተበደርኩ ፍቃድ ወሰድኩ

ሎተሪ ደረሰኝ ብያት ላሊበላ ፣ አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ወሰድኳት ደስስ አላት ፀለየች ፣ ለነዲያን መፀወተች ፣ እጄን ይዛ መረቀቺኝ ።

ከዛ ከተመለስን በኋላ ሶስት ወርም አልቆየች ትንሽ አሞት ሞተችብኝ። ሳለቅስ ፣ ሳዝን ያፅናናኝ እና ያበረታኝ ህልሟን ማሳከቴ ነበር

ቀጠለ ሌላ ፍሬንድ ፦

"አንድ ቀን ክላስ ቀጥቼ ዩኒፎርሜን እንደለበስኩ ጠላ ቤት ደቅ ብዬ አባቴ ከጓደኞቹ ጋር ከች አለ ሳየው ስካሬ ጠፋ ።

ልጄ ነው ብሎ ለፍሬንዶቹ አስዋወቀኝ ። ሃይለኛ ስለነበር እዛው ካልገደልኩ ይላል ብዬ ነበር። ምንም አላለኝም ። እንደውም የጠጣሁበትን ከነ ፍሬንዶቼ ከፈለልኝ ። ቀድሜው ወጣሁ ፦

አላመንኩትም የሚገድለኝን አገዳደል እያሰብኩ ስፈራ ስቸር እቤት አምሽቼ ገባሁ ። እሱ ምንም አላለኝም ።

በሳምንቱ "ጋሻው ዛሬ ትምህርት የለህም አይደል "

"አዎ"
"በቃ ዛሬ አብረን እንዋል አለኝ" እሺ ብዬው የሚሰራበት
አብረን ሄድን

ውሎውን አዋለኝ ። የሆነ ህንፃ ይጠብቃል ፣ ህንፃው ጋ የሚቆም መኪና ይጠብቃል ፣ መኪና ያጥባል ።

የጠበቀበትን እና ያጠበበትን ብር እንዲሰጡት ደጅ ይጠናል ፤ ትንሹም ትልቁም ይጠራዋል ፣ ያዙታል ያን ቀን አባቴ በጣም አሳዘነኝ

ከፊቱ ገሸሽ ብዬ አለቀስኩ

እንዴት እንደሚያሳድገኝ ያኔ ነው የገባኝ ። ምን እያለ እንደመከረኝ ፣ በእኔ ጉዳይ ለምን እንደሚናደድ ገባኝ

የዛ ቀን ህይወቴ ተቀየረ ።

ሌላ ፍሬንድ ቀጠለ ፦

"አንድ ቀን እቃ ጠፍቶኝ ቤታችንን ሳምሰው
የታናሽ እህቴ ዲያሪ አገኘሁት በማላውቀው ምክንያት የማስሰውን ነገር ትቼ ደቅ ብዬ ማንበብ ስጀምር ።

ጥጋቤ ፣ ድፍረቴ እልሄ ተነፈሰ ። የግሩፕ ጠብ አጓጉል ውሎዬ ጣጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ገባኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ መፍራት ጀመርኩ ፤ ለቤተሰባችን ምን ያህል እንደማስፈልግ ማስታወሻዋ ነገረኝ"

ለካ አንዳንድ ቀን ብቻውን ዘመን ያህላል !!
© Adhanom Mitiku

ከመጽሐፍት መንደር💠

26 Oct, 17:08


በዛን ቀን እስከ እኩለ ለሊት ቢጠብቋትም ምስራቅ ተመልሳ አልመጣችም ነበር፡፡ናኦል በጣም ቅር ቢለውም ኑሀሚ ግን ብዙም አልከፋትም፡፡እንደውም የወንድሟን ትኩረት ስለተሻማቻት እያበሳጨቻት ነበር፡፡በማግስቱ ጥዋት አንድ ሰዓት ከመሆኑ በፊት ግን ከእንቅልፋቸው ወዝውዛ የቀሰቀሰቻቸው እሷ ነበረች፡፡ናኦል አይኑን ገልጦ እሷ መሆኗን ሲያውቅ በደስታ ዘሎ ተጠመጠመባትና ጉንጫን ሳማት‹‹ማትመለሺ መስሎኝ ደንግጬ ነበር፡፡››
‹‹ምን ያስደነግጥሀል..?እስከዛሬ ከእሷ ጋር የኖርክ አስመሰልከው፡፡››ኑሀሚ በብስጭት መለሰችለት፡፡
‹‹እህቴ ቃል ገብተሸልኝ ነበር አይደል?››
‹‹እሺ..እንዳልክ፡፡››
‹‹እሺ በእኔ መጨቃጨቁን አቁሙና ተነሱ…ጥሩ ጨላ የሚያስገኝ ስራ ትሰራላችሁ፡፡››
‹‹ምንድነው ?ወንጀል እንዳይሆን?››
‹‹ጎዳና እየኖራችሁ ወንጀል ምናምን ትላላችሁ እንዴ…?ወንጀለኛ እናንተ ሳትሆኑ እናንተን እዚህ ጓዳና ላይ የጣላችሁ ስርአት ነው፡፡ ወንጀለኛ እናንተን ትራፊ እየለቃቀማችሁ እንድትኖሩ አይቶ እንዳላ የሚያልፋችሁ ማህበረሰቡ ነው፤እንጂ እናንተ ለመኖርና ህይወታችሁን ለማቆየት ስትሉ የምትሰሩት ነገር በምንም አይንት ወንጀል ሊባል አይችልም፡፡››
‹‹ትክክል ልትሆኚ ትችያለሽ፡፡ግን ዛፓዎች እጅ ከፍንጅ ሲይዙን እንደዛ ብለው አያልፉንም፡፡ስንሰርቅ ከያዙን ሌባ ፤ ስንገድል ካገኙን ገዳይ ብለው ማሰራቸው አይቀርም፡፡››
‹‹አ…እንግዲያው አለመያዝ ነዋ፡፡አሁን በምትሰሩት ስራ የምታገኙት ለእያንዳንዳችሁ አንድ አንድ ሺ ብር ነው፡፡ትሰራላችሁ ወይስ አትሰሩም…፡፡?›› በወቅቱ ያንን የስራ ግብዣ ከአንደበቷ ሲሰሙ ሁለቱም ጆሮቸውን ነበር ማመን ያቃታቸው፡፡
‹‹እውነትሽን ነው እህቴ?››ናኦል በጉጉት ጠየቃት ፡፡
‹‹አዎ እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እህቴ  እንሳራለን  አይደል…?ሁለት  ሺ ብር  እኮ  ብዙ  ነው፡፡ብዙ  ምግብ  ቡዙ  ልብስ ይገዛልናል፡፡››
ኑሀሚ ዝም ነበረ ያለችው  ..ዝም ስላለች ደግሞ ናኦል አልከፋውም…..ዝም ካለች ወደመስማማቱ እያዘነበለች ነው ሲል ነበር ያሰበው‹‹ተስማምተናል..ስራው ምንድነው?፡፡››
ከኪሷ ጠፍጣፋ የእጅ ሰዓት ምታክል ነገር አወጣችና..‹‹ኩማደር ከዲርን ታውቁታላችሁ…?››
‹‹አዎ እዚህ ሰፈር እሱን የማያውቅ አለ እንዴ..?የእኛ ሰፈር የፖሊስ አዛዥ ነው…፡፡››
‹‹ጥሩ ወደእሱ ቢሮ ትሄዱና የሆነ አሳማኝ ምከንያት ፈጥራችሁ ቢሮው በመግባት ይሄንን ጠረጴዛው ስር ማንም እንዳያየው አድርጋችሁ በማይገኝበት ቦታ ታስቀምጣላችሁ…፡፡››

‹‹እንዴ ምንድነው?ፈንጅ ነው እንዴ?››ኑሀሚ አልፎ አልፎ በፊልም የምታያቸው የአሸባሪዎች የጥቃት አይነቶች ትዝ አላት፡፡
‹‹አረ አይደለም…ይህ ድምፅ መቅጃ ነው፡፡የሚያወራውንና ቢሮ ቁጭ ብሎ ሚሰራውን ስራ ማወቅ ፈልጋለሁ?››
ገራ ገባቸው‹‹ምነው ….ስራውን አትፈልጉም?››
‹‹አይ እሱማ እንፈልጋለን..አንቺ ግን ምን ያደርግልሻል…?››ናኦል እንደማባበል ብሎ ጠየቃት፡፡
‹‹ወንድሜ ከመጀመሪያውም እኮ ይህቺን ልጅ እንዳላመንኳት ነግሬህ ነበር… ምኗም እኮ ቦርኮ አይመስልም፡፡››

ምስራቅ የኑሀሚን ንጭንጭ ችላ ብላ ስለጉዳዩ ማስረዳቷን ቀጠለችበት ‹‹ኮማንደሩ ወንድሜን ሌባ ነው ብሎ አሳስሮብኛል፡፡የሆነ ህገወጥ ነገር ሲሰራ ወይ ጉቦ ሊቀበል ሲደራደር የሚያሳይ የድምፅ መረጃ ባገኝ በዛ አስፈራርቼ ወንድሜን ላስፈታ ችላለሁ፡፡.››
ኑሀሚ ማውራት ጀመረች‹‹እሺ እንሳረለን….ግን….?››
‹‹ግን ምን እህቴ?››ናኦል እህቱ ነገሩን አወሳስባ እንዳታሰነካክለው ሰጋ፡፡
‹‹ስራው ከባድ ነው…ዛፓዎችን ስናጭበርበር ከተያዝን አደጋው ከባድ ነው..››
‹‹በእኔ ይሁንብሽ እህቴ… አንያዝም፡፡እንደውም እኔ ለብቻዬ አደርገዋለው፡፡››
ኑሀሚን ኮስተር ብላ‹‹አይ እንደዛ አይሆንም.. ምናደርግ ከሆነ አብረን ነው የምናደርገው፡፡ የምትከፍይን ገንዘብ ግን ከስራው አንፃር በቂ አይደለም፡፡ለእያንዳንዳችን ሁለት ሁለት ሺ ብር በጠቅላላው አራት ሺብር ትክፍይናለሽ፡፡››አለቻት
ናኦል ደነገጠ‹‹እህቴ ምን ነካሽ…?ያን ሁሉ ብር ከየት ታመጣለች….? ደግሞ ያን ሁሉ ነገር አድርጋልን..ልብስ አልብሳን…አረ ሁለት ሺ ብሩ ይበቃናል…አታያትም እንዴት…››
ምስራቅ ፈገግ አለች…ወደናኦል ተራመደችና ጭንቅላቱን ደባበሰችውና ‹‹ጓረምሳው ስለሰብክልኝ አመሰግናለው፡፡እህትህ እውነቷን ነው፡፡ከስራው አንፃር ክፍያው አንሷል››አለችና እጆን ወደኪሷ ሰዳ የታሰረ ብር መዥርጣ በማውጣት የተወሰነውን ቆጥራ ከውስጡ መዘዘችና‹‹‹ይሄው ሁለት ሺ ብር ነው…ስራውን ስታጠናቅቁ ደግሞ ቀሪው ሁለት ሺ ብር ሰጣችኋለው፡፡ነብሯ ብሩን ተቀበይ..እንደማየው ሀለቃዋ አንቺ ነሽ፡፡››አለቻትና ብሩን እጇ ላይ አሰቀመጠችላት፡፡
ኑሀሜ ኮስተር እንዳለች ብሩን ተቀበለቻትና ቆጠረችው…ሁለት ሺ ብር መሆኑን ካረጋጠች በኃላ ኪሷ ከተተች…፡፡
‹‹በሉ ማታ ተመልሼ እመጣለሁ፡፡››ብላቸው ጥላቸው ሄደች፡፡
መንትዬችም እንዴት አድርገው ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገቡ፤ እንዴት አድረገው የኮማንደሩ በሮ ዘልቀው መግባትና የተሰጣቸውን ሚስጥራዊ ድምፅ መቅረጫ ትክክለኛ ቦታ ማስቀመጥ እንደሚችሉ ለአንድ ሰዓት ያህል ከተማከሩና በመጨረሻ በእቅዳቸው ላይ ሙሉ በሙሉ ከተስማሙ በኃላ ተያይዘው ወደፖሊስ ጣበያው ሄዱ፡፡
ምስራቅ መንትያዎቹ ለአንድ ሰዓት ያን ሁሉ ሲከራከሩ በሆነ ነገር ሲሳማሙ በሌላው ደግሞ ሲጨቃጨቁና የመጨረሻውን እቅዳቸው ላይ ሲስማሙ ሁሉ ካፌ በረንዳ ላይ ቁጭ ብላ በሞባይሏ እየተከታተለቻቸው ነበር፡፡ጥዋት ለሁለቱም ገዝታ የሰጠቻቸው ቢጃማ ውስጥ የተቀበረ ረቂቅ ድምፅና መስል ጭምር በመቅረፅ በስልኳ ሚያስተላልፍ መሳሪያ ነበር፡፡ዝግጅታቸውን ጨርሰው የመጨረሻ ተልዕኳቸውን ወደሚፈፅሙበት ፓሊስ ጣቢያ ሲያመሩ …መከታተሏን ሳታቋርጥ እጇን ወደፔስታሏ በመላክ አንድ ሌላ አነስተኛ ሞባይል በማውጣት ደወለች፡፡
‹‹ሄሎ ኩማንደር?››
‹‹ሄሎ ሀለቃ እንዴት ነሽ?››
‹‹አለው ሚዳቆዎቹ ወደአንተ እየመጡ ነው››
‹‹እሺ ..እስቲ ይወጡት እንደሆነ እንያ፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

26 Oct, 17:07


ከምስራቅ ጋር በወዳጅነት መቀራረብ ብቻ ሳይሆን የስራ ባለደረባም ሆነው እንደሀለቃና ምንዝር ለረጅም አመት ሰርተዋል፡፡ለዛውም በሀገሪቱ የደህንነት መስሪያ ቤት፡፡እርግጥ እሷም ሆነች ወንድሟ ቀጥታ የደህንነት መስሪያ ቤቱ ተወዳድረው አይደለም የተቀጠሩት፡፡በወቅቱ ለእዛ የሚያበቃ እድሜ ላይም ሆነ ሁኔታ ላይ አልነበሩም፡፡ ..የእዛ መስሪያ ቤት አባል የሆኑት በእሷ በኩል ተመልምለው ..በእሷ ጥረት ወደስልጠና እንዲገቡ ተደርገው…በእሷ በኩል ተልዕኮ እየተሰጣቸው ነው፡፡ከዛ ብዙ ብዙ የሚባል ተልዕኮዎችን ተወጥተዋል…ለሀገር የሚጠቅሙ አንዳንዴም የተሳሳቱ ሰራዎችን ሰርተዋል፡፡ ያኔ እዛ በረንዳ ላይ ረዳት አልባ በነበሩበት ጊዜ ካገኘቻቸው በኋላ እንዴት እንደመለመለቻቸው ትዝ አላት፡፡
ኢትዬጵያ/አዲስ አበባ
አንድ ቀን አስራሁለተኛ አመታቸው ላይ ከምስራቅ ጋር በተዋወቁ በሁለተኛው ቀን በየእለቱ ለደምበኞች ጫት የማመላለስ ስራ ሰርተው ከጨረሱ በኃላ ምስራቅ እመጣለሁ ብላቸው ስለነበረች ቦታቸው ላይ ቁጭ ብለው እየጠበቋት ነበር፡፡ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ላይ ምስራቅ እንዳለችው መጣች፡፡ ከመቀመጫቸው ተነስተው በፈገግታ ተቀበሏት፡፡ይዛ የሄደችው አንድ ፔስታል ቢሆንም አሁን ግን ሌላ አንድ ጥብሰቅ ያለ እቃ የታጨቀበት ፔስታል ይዛ መጥታለች፡፡
‹‹ጩጬዎቹ አላቹሁ?›› አለችና ግንቡን ተጠግቶ ያለ ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ ቁጭ አለች፡፡ እነሱም ሌላ ድንጋይ በግራና በቀኝ አስጠጉና መሀከል አድርገዋት ተቀመጡ ፡፡
‹‹ከሁለታችሁ ማነው ታላቅ?››ያልጠበቁትን ጥያቄ ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹እኔ ነኝ…10 ደቂቃ ቀድማታለው››አለ ናኦል፡፡
‹‹እንዴ መንታ ናችሁ እንዴ…?ለነገሩ ጠርጥሬ ነበር…እኩል እድሜ ላይ እንደምትገኙ እንዲሁ በእይታ ታስታውቃላችሁ፡፡››
‹‹አዎ መንትዬዎች ነን፡፡››አረጋገጡላት፡፡ፔስታሉን ከፈተችና እጇን ወደውስጥ ላከች፡፡ ሰማያዊ ሮዝ ቀለም ያለው ሁለት ሙሉ ቢጃማ ከነአላባሹ አወጣችና‹‹ በስምምነት አንድአንድ ተካፈሉ፡፡›› አለቻቸው፡፡
ሁለቱም ፈዘው ይመለከቷት ጀመር፡፡እሷ እራሷ የለበሰችው ልብስ የተቀዳደደና መቀየር የሚገባው ነው…ታዲያ ለምን ለእነሱ?››በወቅቱ ግልፅ አልሆነላቸውም ነበር፡፡
‹‹ምነው? ያልኩት አልገባችሁም እንዴ?እነዚህን ቢጃማዎችን የገዛሁት ለእናንተ ነው፡፡እ… ጎረምሳው የትኛው ይሁንልህ?››
‹‹እህቴ ሮዝ ቀለም ትወዳለች..ሮዙ ለእሷ ይሁን፡፡››
‹‹አንተስ ሰማያዊው ይመችሀል?››

‹‹የእኔ ችግር የለውም..እህቴ ደስ ካላት ደስ ይለኛል፡፡ግን ለምን ለራስሽ ሳትገዢ ለእኛ ገዛሽ??››
‹‹ገዝታ አይመስለኝም…ፖሽራ ነው››ኑሀሚ ግምቷን ተናገረች፡፡
‹‹ተይ እህቴ.. ለምን እንደዛ ትያለሽ….?ብትፖሽረውም እኮ ደግነቷን ነው የሚያሳየው፡፡ለእኛ ከመስጠት ሁለቱን ሸጣ አንድ ለእሷ ሚሆን ልብስ ልትገዛበት ትችል ነበር፡፡››
‹‹ እኔም ያልገባኝ እኮ በደንብ ሳታውቀን ለምን ብዬ ነው…?ምን አስባ ነው?››
በወቅቱ የጎዳና ህይወት ልምዳቸው በጣም ተጠራጣሪ አድርጓቸው ነበር፡፡በዛ ምክንያት ነበር እሷን ዘንግተው እርስ በርሳቸው ክርክር ውስጥ የገቡት፡፡
‹‹ኸረ እህቴ አመሰግናለሁ ነው የሚባለው፡፡››
‹‹ናኦሌ ደግሞ… እዚህ ጓደና ላይ ስንት የማጭበርበር ታሪክ እደሚሰራ አታውቂምናነው.?ለሆነ ነገር እያመቻችንስ ቢሆን…?እኔ ይሄንን ልብስ አልፈልግም፡፡አንተም እንድትቀበላት አልፈቅድልህም…፡፡››
ምስራቅ እጇን ወደ ፔስታሉ ሰዳ ሌላ ነገር አወጣች፡፡በስስ ፔስታል የተጠቀለለ ምግብ ነው፡፡ፊት ለፊቷ መሬት አስቀመጠችና ፈታችው፡፡የሚያስጎመዣ አጥንት ያለው የቅቅል ፍትፍት ነው፡፡እጇን ሰደደችና አንዴ ጠቅለል አደረገችና ጎረሰች፡፡ከፔስታሉ ውስጥ የቀረውን ሁለት ሊትር ውሀ አወጣችና ምግቡ ጎን አስቀምጣ…‹‹አንቺ ነብር የሆንሽ ልጅ…ምግቡ ላይም መርዝ አድርገሽበታል እንዳትይ ነው የቀመስኩልሽ፡፡››በማለት ከተቀመጠችበት ተነሳችና ትናንትም ይዛት የነበረውን ፔስታል አንጠልጥላ በመጣችበት መንገድ ተመልሳ መጓዝ ጀመረች፡፡
‹‹ምስራቅ ወዴት ነው…?እህቴ እኮ ሁሉን ነገር የምትጠራጠረው ለእኔ ስለምትጨነቅ ነው፡፡››
‹‹ችግር የለውም..የምሄድበት ቦታ ስላለ ነው፡፡››
‹‹እና ተመልሰሽ ትመጪያለሽ?››
‹‹ይመስለኛል፡፡››ብላ ሄደች፡፡
መንትዬቹ ተፋጠው ተያዩ‹‹እህቴ ለምን አስቀየምሻት?››
‹‹አላስቀየምኳትም…ስለማናውቃት ተጠራጥሬያት ነው፡፡››
‹‹እሺ በቃ …እስኪ ለኪው፡፡›› ብሎ ሮዝ ቀለም ያለውን ቢጃማ አቀበላት፡፡፡ተቀበለችውና ያደረገችውን ነጠላ ጫማ አውልቃ ሱሪውን በቀሚሷን ከፍ አድርጋ አጠለቀችው
‹‹ከስር ካኔቴራ አድርገሽ የለ ቀሚሱን አውልቂው፡፡››
አወለቀችውና ጀኬቱን ከላይ ለበሰችበት..ወደእሷ ተጠጋና ዚፑን ዘጋላት፡፡እና ከእሷ ራቅ ብሎ አያት፡፡
‹‹ውይ አህቴ ..በጣም ነው ፏ-ፈሽ ያልሽው፡፡አቤት ፀጉርሽ ባይንጨፈረር…፡፡››
‹‹እስቲ የራስህን ልበሰውና እንየው››
‹‹አይ የእኔ ይደርሳል…መጀመሪያ ቡሌውን እንጥለፍ፡፡ሽታው ሆዴን አገለባበጠው፡፡››
‹‹እሺ እንብላ›› አለችና ምግብን አመቻችተው ተቀመጡ፡፡በጣም ጣፋጭ ምግብ ነበር፡፡ሆዳቸው እስኪወጠር ድረስ ነበር የበሉት፡፡እንደጨረሱ ናኦልም ለእሱ የመጣለትን ቢጃማ ለበሰ…..
እንደአማረበት ‹‹የእኔን ትላለህ እንጂ አንተም በጣም አምሮብሀል፡፡››ስትል ነበር ያረጋገጠችለት፡፡
‹‹አይደል…?አሁን የት አግኝተን እናመስግናት?››
‹‹እመጣለሁ ብላለች እኮ !ታገስ፡፡››
‹‹እህቴ ስትመጣ ግን እንደቅድሙ ያልሆኑ ያልሆኑ ነገሮች እንዳትናገሪያት፡፡››
‹‹እሞክራለሁ..፡፡ግን ይህቺ ሴት ምኗም አልጣመኝም፡፡ምን ነካህ ወንድሜ ስለእሷ ምንም አናውቅም አኮ!››
‹‹እኮ እንጠይቃታለና….ስንግባባ ቀስ ብለን እንጠይቃታለን፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

26 Oct, 17:07


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-አስራሁለት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

አማዞን ደን ..ኮሎምቢያ ግዛት
///
ጫካውን እየሰነጠቁ ከአውሬውና ከነፋሳት ጋር እየተጋፉ መጓዝ በጀመሩ አራት ቀን ሆኗቸዋል፡
በጉዞቸው ከዛፍ ዛፍ ሲንጠለጠል አንድ ገራሚ እንስሳ አየች፡፡ትንሽ ነው፡፡ ድመት ነው የሚመስለው፡፡ ግን ጸጉር የለበሰ በመሆኑ ከመጠኑ ገዝፎ እንዲታይ እረድቶታል፡፡ ዝንጀሮም አንበሳም ይመስላል፡፡ከዚህ በፊት በምስል ላይ ፎቶውን እንኳን አይታ አታውቅም፡፡
‹‹ምንድነው ይሄ እንስሳት?››ቁራኛዋን ካርሎስን ጠየቀችው፡፡
‹‹እ ታማሪን ወይም ሮሳሊያ ይባላል፡፡ወይም በቀላሉ ወርቃማው አንበሳ ይሉታል፡፡››

‹‹አዎ እውነትም ወርቃማው አንበሳ፡፡ፀጉሩ እኮ ወርቅ መሳይና አብረቅራቂ ነው…ትክክለኛ ስሙ ይሄኛው ነው፡፡››
‹‹አዎ ዝርያው የዝንጀሮ ቢሆንም እንደምታይው ግን አንበሳ ነው የሚመስለው፡፡የዚህ ፕሪሜት ልዩ ቀለም ምናልባትም በጠንካራ የፀሐይ ብርሃን ጥምረት እና በአመጋገቡ ውስጥ በሚገኙ የካሮቲኖይዶች ብዛት ላይ የተመሠረተ ነው የሚል መላምት አለ።እንደምታይው አስደናቂ ገጽታ አለው: ወፍራም፤ ለስላሳ፤ ደማቅ ቀይ ፀጉር፤እንዲሁም ጥቁር ፊት እና ትልቅ ቡናማ አይኖች ያሉት አስደማሚ ፍጡር ነው››
‹‹ስላየሁት ደስ ብሎኛል፡፡የማልሞት ቢሆን ኖሮ እዚህ መጥቼ ስላየሁት እያንዳንዳንዱ ድንቅ እና አስደሳች ነገር… ስለእንስሳቱና ስለጥቅጥቁ ዳን… ስለሚንዠቀዠቀው የአማዞን ወንዝ ለወንድሜም ለጓደኞቼም በደስታ እንግራቸው ነበር..ግን ምን ዋጋ አለው….››ከገባችበት ጊዜያዊ የደስታ ስሜት ወጣችና ሀዘን ውስጥ ገባች፡፡
‹‹አይዞሽ …እሰክአሁን በህይወት አለሽ ..ለጊዜው ያ በቂ ነው፡፡››አላት፡፡

‹‹እንዳልክ ይሁንልህ››አለችውና ዝምታ ውስጥ ገባች፡፡
እኩለ ቀን ላይ ኣማዞን ወንዝን ታካ የተመሰረተች የደቡብ ኮለምቢያ የጠረፍ ከተማ ከሆነችውና 35 ሺ ኑዋሪዎች ከሚኖሩባት ላቲሲያ ከተማ ደረሱ፡፡ይህቺ ከታማ ሶስት ሀገሮች ማለት ፔሩ ኮሎቢያን ብራዚል የሚገናኙባት ነጥብ ከሆነችው ትሬስ ፎረንቴራስ ትንሽ ወደላይ ፈቅ ብላ ምትገኝ በዓሳ ምርቷ የታወቀች እጥር ምጥን ያለች ከተማ ነች፡፡የኮሎምቢያ መንግስት ግዙፍ የሆነ የዓሳ ምርቱን ከአካባቢው እየሰበሰበ በጀልባ በመጫን ወደ ማአከላዊ የሀገሪቱ ስፋራዎች የሚጫንባት ወሳኝ ከተማ ነች፡፡ከታማዋን በሩቅ ሲያዮት እና ጉዞቸውንም በዛ አቅጣጫ ሲያቀና ቀጥታ ወደከታማው ዘልቀው ሚገቡ መስሏት ተደስታ ነበር፡፡የዛም ምክንያቱ ህዝብ ያለበትና የመንግስት ተቋማት ሚንቀሳቀሱበት ስፍራ ላይ ከደረሰች በተቻላት መጠን ለማምለጠ ትሞክራለች፤ያ ከሆነ ደግሞ ጥረቷ የመሳካት እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ ስሌቱን ስለሰራች ነው፡፡ይሁን እንጂ አጋቾቻ
የገመተቻቸውን ያህል ጥንቃቄ አልባ አልነበሩም፤በዛም ምክንያት ወደከታማዋ አልገቡም፡፡ይልቅስ ከተማዋን በቅርብ ርቀት ታካ አማዞን ጉያ ውስጥ ተወሽቃ ከምትገኝ ነባር ጎሳዎች ወደሚኖሩባት ወደአንድ መንደር ነው ጎራ ያሉት፡፡

‹‹እርግጠኛ ነኝ ይሄ የመጨረሻ የጉዞ መዳረሻችን ነው፡፡››ካርሎስን ነው የምትጠይቀው፡፡
‹‹አይመስለኝም..ግን የተወሰኑ ቀናትን እዚህ የምናርፍ ይመስለኛል››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹በሩቅ ወደምትታየው ከተማ ምንገባ መስሎኝ ነበር››
‹‹እ..ወደ ላቲሲያ ማለትሽ ነው..ወደእዛ አለመግባታችን ጥሩ ነው…ለአንቺ ምንም ሚጠቅም ነገር አይገኝበትም…ከኑዋሪዎቹ ከግማሽ በላይ የእኛ ሰውዬ ሰዎች ናቸው››

ተስፋ ቆረጠችና… ዝም አለች፡፡..የቡድኑ ሰዎችን ለመቀበል ሶስት የሆኑ የመንደሩ ሰዎች መጡና አወሯቸው፡፡ ከተወሰኑት ጋር የሞቀ ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ አንድ ወለሉ በአየር ላይ የተንጠለለ በስሩ ውሀ የሞላበት በጣውላ እርብራብ የተሰራ የሳር ክዳን ቤት ከፊት ለፊታቸው ይታያል፡፡ወደዛው መጓዝ ጀመሩ፡፡ቤቱ ሰፋ ያለ ግን ደግሞ እቃ አልባ ነበር፡፡ቁራኛዋ ሰንሰለቱን ከላዩ ላይ አላቀቀና ለብቻዋ ተወላት፡፡ሁሉም በተርታ መቀመጫ ይዘው ተቀመጡ…ምግብ ቀረበላቸው፡፡ ሁሉም ተርበው ስለነበር የምግብ አይነቱ ሳያስጨንቃቸው በፍቅር በሉ ፡፡የሚጠጣ ነገር ቀረበላቸው…ጠንከር ያለ የአልኮል መጠጥ ነው፡፡እሷ መጠጣት አልፈቀደችም፡፡፡ውሀ ቀረበላት፤እሱን ጠጣች፡፡የምግብ ስርአቱ ካለቀ በኃላ እሷን እዛው ቤት ውስጥ ተዋትና ከውጭ ቆልፈውባት ወጥተው ሄዱ፡፡

ቤቱን ክፍት ትተውት ቢሄዱም ወደምትሄድበት ቦታ የላትም፡፡መቼስ በቃ ተመልሰሽ ሂጂ ቢሏት እንኳን የአራት ቀን መንገድ በእንደዛ አይነት ጥቅጥቅ የአማዞን ደን ከጇጓርና ከአናኮንዳ ጋር እየታገለች…አረንጎዴ መርዛማ እንቁራሪቶችና ሰውነት ላይ ከተጣበቁ ማይላቀቁ ጉንዳኖችን ተቋቁማ ወደኃላ ተመልሳ ፔሩ ገባለው የሚል ግምት የላትም፡፡እርግጥ ወደፊት ቀጥላ በአምስት ኪሎ ሜትር እርቀት ላይ ከምትታየው ላቲሲያ ከተማ ልትሄድ ትችላለች፡፡ግን ሙሉ ከተማው የራሳቸው የጋንግስተሮቹ ግዛት እንደሆነ ካርሎስ በግልፅ ነግሯታል...ምክሩን ችላ ብላ ብትሄድና ምንም አይነት የመንግስት ተቋም ሆነ የሚታደጋት ተቋም በቦታው ባይኖርስ…?፡፡ጠቅለል አድርጋ ስታስበው ከዚህ አሁን ካለችበት ስፍራ አምልጦ ነፃ መውጣት የማይተገበር ምኞት ሆኖ ነው ያገኘችው፡፡
ደክሞት ስለነበረ እቤቱ ውስጥ ያለች አንድ መተኛ ፍራሽ ነገር ላይ ሄዳ ጋደም አለች፡፡፡ሰውነቷን በቀላሉ እንዳሳረፈችው አእምሮዋን ልታሳርፍ አልቻለችም፡፡ በእነዚህ ሰዎች እጅ ከገባች ቀን ጀምሮ እንዲህ ለብቻዋ በመሆን ጥቂት ሳዕታትን ባገኘች ቁጥር ወዲያውኑ ሀሳቧ በሮ ወንድሟ ጋ ነው የሚሄደው፡፡የትናንት ትዝታዋ ጋር ነው የሚለጠፈው፡፡ናኦል ይሄኔ ለአራት ቀን ድምፆ ሲጠፈበት እና ስልኳም አልሰራ ሲለው የሚያደርገው ጠፍቶት መስሪያ ቤቷ ሄዶ እህቴን ውለዱ እያለ እያስጨነቃቸው አንደሚሆን ገመተች..ብቻ በዛ ችኩል ባህሪው የሆነ ሰውን ውለዷት ብሎ አፍንጫ እንዳይሰብር ነው የሰጋችው፡፡ምን አልባትም ምስራቅ ጋር ሊሄድ እንደሚችል ገመተች፡፡እንዲህ አይነት ጭንቅ ውስጥ ሲገባ ከምስራቅ ቀድሞ ወደአእምሮ የሚመጣ ሌላ የተሻለ የሚቀርባቸውና የሚረዳቸው ሰው እንደሌለ ታውቃለች፡፡እሷም በእሱ ቦታ ብትሆን እንደዛ ነው የምታደርገው፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

25 Oct, 18:19


"ልማድሽ ነው"

"ባለፈው እንደእብድ ያረገሽን ዘፈን አገኘሁት እኮ ቆይማ ልላክልሽ" ብሎ ስልኩን ሊያወጣ ሲል "የትኛውን ዘፈን አለችው ግራ ተጋብታ

"እንደውም ዜማውን ብቻ የሆነ ካፌ ሰምተሽው ምነው ባገኘሁት ብለሽ ሲቆጭሽ የነበረው ዘፈን..." አላት ቅሬታ እየተነበበት "እ እሱ ነው እንዴ? ፈልጌ ሳጣው ሌላ አገኘሁ እኮ እንዴት ደስ እንደሚል ግጥሙ ብትል ዜማው..." እያለች ስታብራራለት በትዝብት ሲያያት ቆየና

"እ ደስ አይልም?!" አለችው ዘፈኑን ከፍታ ምላሹን እየጠበቀች "ልማድሽ ነው አንዱን ስታጪ ሌላ መውደድ" አላት

ስለዘፈኑ መስሏት ምንም አላለችም ነበረ ኋላ ማታ ላይ ሲቆረቁራት አደረች እንጂ...


ናኒ

ከመጽሐፍት መንደር💠

23 Oct, 07:51


''ደብረሲናን እንዳታሳልፈኝ'' ይላሉ አንድ እናት ወደደሴ እየሄዱ:: ደጋግመው ''ደብረሲናን እንዳታሳልፈኝ'':: ትንሽ እንደሄዱ ''ደረስን ደብረሲና?'' ሲሉ ረዳቱ ''ውይ እማማ አለፍነውኮ'' በጩኸት ያናጉታል መኪናውን::
''አዙረው: ደብረሲና መልሰኝ!'' ተሳፋሪው ሁሉ የሴትዮዋን ሁኔታ አይቶ እና በረዳቱ መዘናጋት ተበሳጭቶ ''በቃ መልሳቸው'' ይባልና ይዞራሉ::

''እማማ ደርሰዋል ደብረሲና''
''ደረስን?'
"አዎን"
"ይሄ ነው ደብረሲና?"
"አዎን"
መሃረባቸውን ፈትተው መድህኒት ውጠው ቁጭ::
"እማማ ይውረዱ እንጂ"
"እህ ለምን? በል ንዳው አሁን?"
"ለምን ይውረዱ እንጂ?"
"ልጄ መድኃኒትሽን 'ደብረሲና ላይ ዋጪ' ብላኝ ነው:: በል ንዳው ሳይመሽ"
ዴግም ናችሁ አይደል? 🤗

Yiftusira Mitku

ከመጽሐፍት መንደር💠

22 Oct, 01:56


#አይ_መርካቶ

አገር ከየጎራው ወጥቶ
አንቺን ብሎ ነቅሎ መጥቶ
ግሳንግሱን ጓዙን ሞልቶ
ኁልቁ መሳፍርትሽ ፈልቶ
ባንቺ ባዝኖ ተከራትቶ
እንደባዘቶ ተባዝቶ
ተንጠራውዞ ዋትቶ ዋትቶ
አይ መርካቶ

የምድር አለም የእንጀራ እናት
ላንዱ ርካሽ ለሌላው እሳት
ላንዱ ፍትሃት ላንድ ምትሃት
ላንዱ ሲሳይ ላንድ ፍርሃት
ላንዱ ተስፋ ላንድ ስጋት
የግርግር የሆይታ ቋት

አይ መርካቶ

ያንዱን ወስዶ ላንዱ ሰጥቶ
ያንዱን ገፋፎ ላንዱ አብልቶ
አንዱን ነስቶ ላንዱ አድልቶ
ስንቱን ፈርቶ ስንቱን ሸሽቶ
ባፈ ጮሌ ተሸልቶ

ፀጋዬ ገብረ መድህን

እኔ ማርያምን አሳዘኑኝ
በዚህ ኑሮ ላይ ሀብት ንብረታቸውን ሲያጡ ....
በእውነት ያሳዝናል ብቻ ከዚህ በላይ ከጻፍኩ ...... 😥
ብቻ ዝምምምም 😥 ቅዱስ ሚካኤል ይድረስላችሁ፥

ከመጽሐፍት መንደር💠

21 Oct, 17:32


ታናሽ እህቴ ናት በአስራ ሶስት አመት እበልጣታለሁ ። እሷ ላይ ያለኝ ስልጣን የአለቃ ነው ። 'exercise' የማደረገው ስልጣን ብዙ ነው የአፍሪካ መሪዎች  ዜጎቻቸው ላይ ካላቸው  ስልጣን አያንስም ። እሷም ስልጣኔ ነው ብዬ 'exercise' የማደርገውን በፀጋ ተቀብላለች ።

ልጄ ትመስለኛለች ምግብ በጋራ ስንበላ ቀድሜ ነው በቃኝ የምለው ። ከሷ ጋር እንዳልሻማ ፍቅሬ እና ሃላፊነቴ ይገታኛል ።

ሁኔታዋን  አየዋለሁ ሲዶክካት፣ ስትደሰት እንቅስቃሴዋን  አስተውላለሁ  ። ከጓደኛዋ እንዳታንሳ  'Invest' አደርግባታለሁ ።

የሆነ ፊልም እያየን  መጥፎ ገፀባህሪ  ስታይ "ኤፍሬም ፊልም ስለሆነ ነው እንጂ:  እንደዚህ አይነት ሰው በትክክለኛ ህይወት የለም አይደል? " ትላለች

ሰው የማርያምን ስም ጠርቶ የሚዋሽ አይመስላትም ፣ ለገንዘብ ብሎ ሰው ጓደኛውን የሚክድ አይመስላትም ፣ የውሸት ለቅሶ ያለ አይመስላትም ። ንፁህነቷ ያስደነግጠኛል ። ብስለት የሚባለውን እውቀት ማጥመቅ ፈልጌ አጠማመቁ ግራ ይገባኛል ።

ስለዓለም ክፋት መንገር እጀምር ና አለምን የምታይበት መነፅር እንዳይንሸዋረር እሰጋለሁ ።

'Feminist ' አደረገችኝ። ትሁቴን እያሰብኩ መደፈር፣ ድብደባ፣ ጭቆና እቃወማለሁ ። ትሁቴን  ስለማስብ ሴት አታልሎ ወደ አልጋ መውሰድ አልችልም ። ትሁትን እያሰብኩ  ገራገር  እንስቶች ላይ 'Advantage ' ለመውሰድ አልሞክርም ።

ትሁቴ የመጀመርያ ልጄ ነች ። በሷ ጉዳይ አልራቀቅም  ፣ በሷ ምክንያት ሴቶች ላይ በደል አልሰራም ።

ትሁቴ እንዳትኮርጀኝ ሰክሬ አልንገላወጅም ፣ የማይረባ ጓደኛዬን እቤታችን አላመጣም ፣ ትልቅ ለመሆን እባትላለሁ ።

የአንዳንድ ታናሽ አሻራ እንደ መምህር አይነት ነው !!
   © Adhanom Mitiku

ከመጽሐፍት መንደር💠

21 Oct, 15:53


‹‹እዛ ነዳጅ ማደያው ጎን ዳስ ውስጥ ቆቆር ፤አሳምብሳና ሻይ ምናምን ምትሸጥ ጀለሳችን ነች፡፡ሳንቲም ሲኖረን እሷ ጋር ነው የሚንሄደው፡፡ጥሩ ልጅ ነች፡፡ ሳንቲም ሲጎድለን ሁሌ ትሞላልናለች፡፡››ናኦል አብራራላት፡፡
‹‹ጥሩ ነዋ በቃ እንሂድ ››ተስማሙና ወደእዛ ሄዱ፡፡ ሶስቱም በደንብ እስኪጠግቡ ቁርሳቸውን በሉ፡፡ እንደወጡ…‹‹በሉ ደህና ዋሉ፡፡›› ብላ ነበር የስንብት ቃል ያሰማቻቸው፡፡
ሁለቱም ያልጠበቁት ነገር ስለነበር ደነገጡ…‹‹ምነው ልትሄጂ ነው?››ናኦል በቅሬታ ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ ምነው?››
‹‹አይ ጥሩ ልጅ ነበርሽ….ባትሄጂ ደስ ይለን ነበር››
ፈገግ እያለች‹‹እሺ አንተ ደስ ካለህ ተመልሼ መጣለሁ፡፡››አለችው
‹‹በእውነት?››
‹‹አዎ የሆነ ቦታ ደርሼ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ እመጣለሁ፡፡››
‹‹እሺ ቸው.. እንዳትቀሪ››
‹‹እሺ በሉ ደህና ሁኑ፡፡›› ፊቷን አዙራ በተቃራኒው አቅጣጫ ነበር መጓዝ ጀመረች፡፡እንሱም ፊት ለፊታቸውን ይዘው ሶስት የሚሆኑ እርምጃዎች ከተራመዱ በኃላ ናኦል ድንገት ዞር አለና
‹‹እህቴ›› ሲል ተጣራ…ዞር አለች፡፡‹‹እ ምነው?››
‹‹ስምሽን እኮ አልነገርሽንም፡፡››
‹‹ምስራቅ እባላለሁ፡፡››ስሟ ከአንደበቷ ተስፈንጥሮ ሲወጣ ወዲያው ነበር ልቡ ላይ አርፎ ቅልጥልጥ በማለት ከመላ ሰውነቱ የተዋሀደው …..‹‹ምስራቅ…አንፀባራቂና በብርሀን የተሞላ ስም››ይላል ሁል ጊዜ፡፡ከዛ ‹‹የእኔ ደግሞ ናኦል ነው …የእህቴ ደግሞ ኑሀሚ፡፡››ብሎ ነበራት፡፡
‹‹እሺ ቸው ናኦል››ፊቷን አዞረችና እርምጃዋን ቀጠለች… ጎኑ ያለችው እህቱ በክርኗ ጎሰመችው
‹‹እንዴ ምን እየሆንሽ ነው…?ምን አደረኩ?››ግራ ተጋብቶ ጠየቃት፡፡

‹‹እህቴ አልካት እኮ፡፡››
‹‹እና ምን ችግር አለው?››
‹‹አንተ እኔን በምትጠራበት ስም ሌላ ትናንት ያወቅካትን ሴት ትጠራለህ…?ሆዳም ነገር ነህ፡፡ አሳንቡሳ ስለጋበዘችህ ነው አይደል?፡፡››የቅናት ወቀሳ ወቀሰችው፡፡
‹‹አይ አይደለም..ቆንጆ ስለሆነች ነው፡፡››አላት
‹‹ቆንጆ ብትሆንም እኮ ትልቅ ልጅ ነች… ሰላሳ አመት ይሆናታል፡፡››
‹‹አትዋሺ 25 ቢሆናት ነው፡፡››
‹‹ሀያ አምስት ቢሆናትም እኮ ትልቅ ነች ማለት ነው… አንተ እኮ ገና 11 አመትህ ነው…ታምራለች ትላለህ እንዴ?››አሾፈችበት፡፡
‹‹አሁን ስራ እስኪደርስ የት እንሂድ?››
በወቅቱ ሁለቱም በቀን ሰላሳ ብር የሚያስገኝላቸው ቋሚ ስራ ነበራቸው፡፡ስራው እዛው ሰፈር ካለ ጫት ቤት ጫትና መሰል ዕቃዎችን ደንበኛ ለሆኑ አምስት ሚሆኑ ሰዎች እንዳንዴም ቁጥራቸው እስከአስር ይሄዳል…ከ6-8 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ በየቤታቸው ማድረስ ነበር፡፡ሁሉም ቤት የሚሄዱት አብረው ነው፡፡ከዛ የእለቱን ስራቸውን ሲያጠናቅቁ የጫት ቤቱ ልጅ 30 ብር ይሰጣቸዋል፡፡ታዲያ ብቸኛ ገቢያቸው ያ ብቻ አልነበረም..የሚወሰዱላቸውም ሰዎች አምስትም አስርም ብር ይሰጧቸው ስለነበር..በየቀኑ 50 ስልሳ ብር አካባቢ አንዳንዴም ከዛ በላይ ያገኛሉ፡፡
እዛ መስቀል አደባባይ በቀዘቀዘ ድንጋይ ላይ ተጎልቶ የሚያመነዥገውን ትዝታ ሳይጨርስ የስልኩ ጥሪ አባነነው፡፡የማያውቀው ስልክ ነው፡፡በዛ ውድቅት ለሊት ከሷ ውጭ ሌላ ሰው እንደማይሆን እርግጠኛ ነው ፡በፍጥነት አነሳው፡፡
‹‹ሄሎ 22 ጎላጎል ህንፃ ፊት ለፊት ከ30 ደቂቃ በኃላ.. ትችላለህ?

‹‹አዎእችለለሁ፡› ስልኩተጠረቀመ፡
ድንግርግር አለው፡፡ናፍቀዋለች፡፡ብዙ የመግቢያ ሰላምታና የናፍቆት ንግግር ጠብቆ ነበር፡፡ምን አይነት ችግር አጋጥሞህ ነው? ብላ እንድትጠይቀውም ፈልጎ ነበር..ግን ከምኞቱ አንዱንም አላሞላችለትም፡፡‹‹ዋና መደወሏ ነው›› አለና ከተቀመጠበት ተነሳ፡፡እግሩን መንቀሳቀስ ግን በቀላሉ አልቻም፡፡ድንዝዝ ነበር ያለው..እንደምንም ለማፍታታትና ለመራመድ ከሁለት ደቂቃ በላይ አስፈልጎት ነበር፡፡መኪና ውስጥ ገባና ወደተባለው አቅጣጫ መንዳት ጀመረ፡፡በለሊት በአዲስአበባ ጎዳና መንዳት እንዴት ደስ ይላል?››ሲል አሰባ፡፡ከፊት የሚደነቀር መኪና የለ ፤በየደቂቃው ፍሬን እምቅ አድር መያዝ የለ፤ ከኃላ ሚያንባርቅ የመኪና ጥሩንባ የለ ››በማለት በነፃነት በመንዳቱ እተደነቀ የተባለበት ቦታ ከተባለበት ሰዓት ቀድሞ ደርሶ መኪናዋና ራቅ አድርጎ በማቆም ይጠብቅ ጀመር፡፡ከ10 ደቂቃ በኃላ አንድ ጥቁር መርቼዲስ ከወደ ቦሌ አቅጣጫ መጣችና አደባባዩን መዞር ጀመረች፡፡የመኪናውን የፊት መብራት ቦግ ብልጭ አድርጎ በማብራት ምልክት ሰጠ..እሷ ከሆነች ይገባታል፡፡ለረጅም ጊዜ አብረው የስለላ ስራ ይሰሩ በነበረበት ወቅት ከሚጠቀሙባቸው በርካታ የመግባቢያ ኮዶች መካከል አንዱን ነው የተጠቀመው፡፡መርቸዲሶ ቀጥታ ወደእሱ በመምጣት ዞራ ከእሱ ኃላ ቆመች፡፡ቀስ ብሎ ወረደና ወደ እሷ ሄደ፡፡ገቢናው ተከፈተለት፡፡ገባና ዘጋው፡፡ከቅድሙ የስልክ ልውውጥ በመነሳት ኮስተር ያለ ነገር ነበር የጠበቀው፡፡
በተቀመጠችበት ሆና ሁለት እጆቾን ዘረጋችና አንገቱ ላይ ተጠመጠመችበት፡፡ፊቱን አንገቷ ሰር ደፈቀው…ከገላዋ የሚወጣው ጠረን አፍንጫው ውስጥ ተመሰገ.. ወደውስጥ በጥልቀት ሳበው፡፡እየቃተተ በሚመስል የሰለለ ድምፅ‹‹በጣም ናፍቀሺኝ ነበር››አላት፡፡
ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ አይቶ እንደደነገጠባት የ12 ዓመት ልጅ አይደለም አሁን ጉርምስናውና በማጠናቀቅ ላይ ያለ የ27 አመት ሙሉ ወጣት ነው፤እሷ ደግሞ የ43 ዓመት ጎልማሳ፡፡አሁን ስለእሷ የሚሰማው የፍቅር ስቃይ አካላዊም ስነልቦናዊም ጭምር ነው፡፡ልቡም ነፍሱ ናቸው በእኩል የሚንሰፈሰፉላት፡፡ከእቅፎ አወጣችውና ጉንጩን ሳመችው፡፡እሱም በተመሳሳይ ሳማት፡፡
‹‹አርጅተሀል እኮ…ምነው አገባህ እንዴ?››
‹‹እንዴት ላገባ ችላለሁ?››አላት፡፡
‹‹እኔ እንጃ ጅርግፍግፍ ስትል ምን አልባት ሰርግ ሳትጠራኝ አግብተህ እንደሆነ ብዬ ነዋ፡፡ ››
‹‹እህቴ እንደዛ አይደለም ባክሽ …ችግር ላይ ነች፡፡››

‹‹እሱንማ መልዕክት ስትልክልኝ ነው ችግር ላይ መሆንህን ያወቅኩት ….ለመሆኑ ምን አይነት ወንጀል ውስጥ ገብተህ ነው?››የጠረጠረችውን ጠየቀችው፡፡በእሷ ሀሳብ ያው እንደልማዱ ከሆኑ ወንጀለኛ ብድኖች ጋር ተቀላቅሎ የሆነ ስራ ውስጥ በመግባት አሁን መውጫ መንገድ አጥቶ ወይ አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ እሷ ከማጥ እንድታወጣው ፈልጎ እንደሆነ እርግጠኛ ሆና ነው ልትረዳወው የመጣችው፡፡ከዚህ በፊትም ከተመሳሳይ ማጥ ሶስት አራት ጊዜ አድነዋለች..አሁንም ከእሷ አቅም በላይ አይሁን እንጂ ታደርገዋለች፡፡ለእሷ እሱን መርዳትና ማገዝ እንደምርጫ ሳይሆን እንደግዴታ ነው፡፡

‹‹እህቴ በለፈው እኮ ቃል ገብቼልሻለሁ…አንቺን ችግር ውስጥ የሚያስገባ ምን አይነት መጥፎ ነገረ እንዳማልሰራ ነግሬሽ ነበር… ያንንም እስከቻልኩት ድረስ ቃሌን ጠብቄ መቀጠል ነው የምፈልገው፡፡››
እና ታዲያ በዚህ ውድቅት ለሊት መልዕክት የላክልኝ እንዳቅፍህና ጉንጮችህን እያገላበጥኩ እንድስምህ ነው እንዴ…?.እንደዛ ከሆነ ችግር ውስጥ ነህ፡፡››ብስጩዋ ሴት ከውስጦ ብቅ አለች፡፡
‹‹አረ አይደለም ..እህቴ ..ኑሀሚ ችግር ላይ ነች፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

21 Oct, 15:52


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-አስራአንድ
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ከዛ በኃላ ኑሀሚ በመገረም እንደተዋጠች ፊቷን አዙራ ወደወንድሟ ነበር የተመለሰችው፡፡ እንደደረሰች ጆንያውንና አሮጌ ብርድልብሱን ገለጠችና ወንድሟ እቅፍ ውስጥ ገባች፡፡
‹‹ምነው አኮረፍሽ?››
‹‹አረ ይህቺ ደነዝ ነች…ጭራሽ ታሾፋለች፡፡››
‹‹ይገልሻል አላልሻትም?››
‹‹አይገባትም አልኩህ እኮ …የጨለለች ሳትሆን አትቀርም ፡፡››
ወዲያው ንግግራቸውን ሳያገባድዱ ነበር የቾንቤ ድምፅ የተሰማው .. እያጓራና እየለፈለፈ ወደእነሱ እየቀረበ ነበር…‹‹ተሸፋፈኚ ..ተሸፋፈኚ….››ናኦል እህቱን አስጠነቀቀ፡፡ሁለቱም ተሸፋፈኑና  አይኖቻቸውን  በብርድልብሱ  ቀዳዳ  አጨንቁረው  የሚሆነውን  ለመመልከት ዝግጁ ሆኑ፡፡እንደጠበቁት ቾንቤ እየለፈለፈና እየፎከረ ቀጥታ ወደልጅቷ ነበር የሄደው፡፡ዘና ብላ ከተቀመጠችበት ነቅነቅ ሳትል እየጠበቀችው ነበር፡፡
‹‹ወንድሜ አለቀላት..ስታሳዝን››ኑሀሚ በቀጣይ የሚሆነውን እየገመተች ተሸማቀቀች፡፡

ቾንቤ ደረሰባትና ዘፍ ብሎ ስሯ ቁጭ አለ፡፡ያ ሁሉ ሲሆን ከልጅቷ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እየታያቸው አልነበረም ፡፡
‹‹ምንም እየተንቀሳቀሰች እኮ አይደለም፡፡››
‹‹አዎ መሞት እንደምትፈልግ ነግራኛለች…እንዲገድላት ነው የምትፈልገው፡፡›› ከልጅቷ ጋር ባደረገችው ንግግር የገባት የመሰላትን ለወንድሟ አብራራችለት፡፡
ቾምቤ ሲያቅፋት ተመለከቱ…ወደኃላ ሊያስተኛት እየሞከረ ነበር፡፡ከዛ እጇን አዙራ ስታቅፈው አዩ…..‹‹እንዴ ልጅቷ እራሷ መከካት ፈልጋለች መሰለኝ?›› ናኦል ነበር ተናጋሪው፡፡
ቀስ ብላ ወደኃላ አስተኛችውና እሷ ተነስታ ቆመች፡፡ከዛ ልብሷን ረገፍ ረገፍ አደረገችና ስሯ የነበረውን አንድ ጥቁር ፔስታል ይዛ ሁለት ሜትር ያህል ከእሱ ራቅ አለችና ተቀመጠች..ቾምቤ እንደተዘረረ ነው..እየተንቀሳቀሰ አይደለም፡፡››
‹‹ወይኔ አይንቀሳቀስም እኮ፡፡››
‹‹ምን አደረገችው?››
‹‹እኔ እንጃ…ሁለቱም ከተሸፋፈኑበት ገልጠው ወጡ፡፡አስር ደቂቃ ያህል ጠበቁ….፡፡ምንም የተለየ ነገር እየታያቸው አልነበረም…፡፡እንደውም ልጅቷ ከፔስታሏ ውስጥ ሻርፕ ነገር አውጥታ ፊቷን ተሸፋፈነችና ሸርተት ብላ ግንቡን ተደግፋ እንደመተኛት አለች፡፡
‹‹እንዴ ገደላት ስንል ገደለችው እንዴ….?››እሱ የለበሰውን ከላዩ ገፎ ተነሳ
‹‹ወዴት ነው?››ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹ …ሄጄ ላጣራ?›››

‹‹ቆይ አብረን እንሂድ ፡፡››አለችና እሷም ተነሳች፡፡ፈራ ተባ እያሉ ተጠጉ፡፡ ደረሱ…. ቾምቤ እጥፍጥፍ ብሎ እንደተኛ ነበር፡፡
‹‹እ ጩጬዎቹ ምንነው?››
‹‹ደየመብሽ እንዴ?››ናኦል ፈራ ተባ እያለ ጠየቃት፡፡
‹‹ጎንበስ ብለህ እየው…..እኔ እንዲተኛ ብቻ ነው ያደረኩት፡፡ሞቶም ከሆነ የእኔ የእጅ የለበትም፡፡››
‹‹ካራቲስት ነገር ነሽ እንዴ..?እንዴት አድርገሽ ቆለፍሽው?››
ናኦል ጎንበስ አለና ትንፋሹን አዳመጠው፡፡እውነትም አልሞተም፡፡ ትንፋሹ በደንብ ይሰማል፡፡
‹‹አይ ሰላም ነው፡፡››
‹‹ኑ እስቲ ከጎኔ ተቀመጡ፡፡››
ሁለቱ ታዳጊዎች እርስበርስ ተያዩ፡፡ የዚህችን እንግዳ ሴት ግብዣ እንቀበል ወይስ ይቅርብን ሚለውን በአይን እየተነጋገሩ ይመስል ነበር፡፡ከዛ እንደተግባባ ሰው ወደእሷ ቀረቡና እሱ በቀኟ እሷ ደግሞ በግራዋ በኩል ተቀመጡ፡፡
‹‹እዚህ ቆያችሁ…ማለቴ በርንዳ ላይ?››ጠየቀቻቸው፡፡
‹‹አዎ አንድ አመት ሊሞላን ነው፡፡››
‹‹ታዲያ አይተናኮሏችሁም…በተለይ አንቺን፡፡››
‹‹አይ እንደመጣን ሰሞን ያስቸግሩን ነበር..ግን እዛ ፖሊስ ጣቢያ የሚሰራ ፓሊስ አባታችንን በደንብ ያውቀው ነበር..እና እዚህ ሰፈር ላሉት ጉልቤዎች በጠቅላላ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷቸዋል፡፡አንድ ሰው እኛን ቢያጠቃ ሁሉንም እንደሚያጠፋችው ስለነገራቸው አይነኩንም፡፡››በሰላም እየኖሩ ያሉበትን ምክንያት በግልፅ አብራሩላት፡፡
‹‹ለጊዜው ጥሩ ነው..ግን እዚህ ጎዳና ላይ እስከኖራችሁ ድረስ በሌላ ሰው ላይ ተማምናችሁ እስከመጨረሻው  ከጥቃት  ተጠብቃችሁ  መኖር  አትችሉም፡፡ያላችሁት  ፖሊስ  አዛዥ የመንግስት ቅጥረኛ ነው፡፡መንግስት ደግሞ ነገ ተነስቶ ሌላ ወረዳ ወይም ሌላ ከተማ ሊመድበው ይችላል፡፡የዛን ጊዜስ ምን ትሆናላችሁ?››በውድቅት ለሊት ቀን እንኳን ቢሆን መመለስ ሚከብድ ጥያቄ ነበር የጠየቀቻቸው፡፡፡
‹‹እውነትሽን ነው..ይሄ ጉዳይ ሁሌ ያስጨንቀኛል….ለእኔ ሳይሆን ለእህቴ?››የሚል መልስ እንደሰጣት ያስታውሳል፡፡
‹‹እንዴ እንዲህ እንደምታስብ እኮ አንድም ቀን ነግረኸኝ አታውቅም…?›› ኑሀሚ በጭለማው ውስጥ አፈጠጠችበት፡፡
‹‹እንዴት እንዲህ ብዬሽ እንድትፈሪ አደርጋለሁ?››
ልጅቷ ቦርሳዋን በረበረችና ትንሽ የመጠጥ ብልቃጥ በማውጣት ክዳኑን አሽከርክራ ከፈተችና ተጎነጨችለትና መልሳ በመክደን ከፊት ለፊቷ አስቀመጠች፡፡
‹‹የት ነበርሽ..?ማለቴ እዚህ ሰፈር እንዴት ልትመጪ ቻልሽ?››
‹‹እንዲሁ በዚህ ሳልፍ ሰፈሩ ደስ አለኝና እዚሁ አረፍ አልኩ፡፡››
‹‹እና ነገ ትሄጂያለሽ ማለት ነው?››
‹‹እኔ እንጃ… ሂጂ ሂጂ ካለኝ እሄዳለሁ፡፡››
ናኦል‹‹ብትቆይ ግን ደስ ይለኛል፡፡›› አላት፡፡እንደዛ ያላት ልጅቷ በእድሜ በጣም ታላቁ ብትሆንም ገና እንዳያት በጣም ስለወደዳት ነበር…የዛን ጊዜ ስለእሷ የተሰማው ስሜት ዛሬም ድረስ በልቡ ላይ ተቋጥሮ እንደቆረቆረው ነው፡፡
ዞር ብላ አየችውና እጆቾን ዘርግታ ፀጉሩን እያሻሸች‹‹ጎረምሳው…ተከየፍክብኝ እንዴ?››ነበር ያለችው፡፡
እንደማፈር አለና …አቀርቅሮ ዝም አላት፡፡በወቅቱ ብዙ ነገር ሊመልስላት ፈልጎ ነበር፡፡ግን ከንፈሮቹ ተነቃንቀው ቃላት ከአንደበቱ ማውጣት አልቻሉም፡፡
‹‹አይዞኝ ስቀልድ ነው፡፡ለማንኛውም አሁን ሂዱና ተኙ፡፡.ነገ እናወራለን፡፡››
‹‹እሺ›› አሉና ሁላቱም ከግራና ከቀኞ ተነስተው ባዶ መሬት ላይ ዘና ብሎ በመዘረጋጋት ተኝቶ እያንኳራፋ ያለውን ቾንቤን በጎሪጥ እያዩ በስሩ አልፈው ወደመኝታቸው ሄዱ፡፡ኑሀሚና ናኦል ጥዋት ተነስተው አካባቢውን ሲቃኙ የለሊቷ ልጅ ተነስታ ልክ እንደደላው የቤት ልጅ ስፖርት እየሰራች ነበር ያገኞት፡፡…ሳንቾ በአካባቢው የለም፡፡ሌሎች ጓደኞቻቸው የተወሰኑት ተኝታዋል…የተቀሩትም ወደሚሄድበት ሄደዋል፡፡ለብሳው ያደሩትን አሮጌ ብርድልብስ እና ጆንያ ከስር የሚያነጥፉትን ካርቶን ስብስበውና አጣጥፈው ወደጥግ በማድረግ ዘወትር እንደሚያደርጉት በላዩ ላይ ድንጋይ ጭኑበት እና ወደልጅቷ ሄዱ ፡፡
‹‹እ ጩጬዎች ..ተነሳችሁ፡፡››በሚል ጥያቄ ነበር የተቀበለቻቸው፡፡
‹‹አዎ…ቡሌ ፍለጋ ልንሄድ ነው… ትመጪያለሽ?››
‹‹አዎ…››አለችና እስፖርቷን አቋርጣ ..ፔስታሏን ያዘችና ተከተለቻቸው፡፡
‹‹እ የት ነው ምንበላው?
ሁለቱም አፍጥጠው አዮት‹‹እንዴ ገና ሆቴል ሄደን ተመላሽ ጠይቀን ነዋ››ኑሀሚ ነበረች በመኮሳተር የመለሰችላት፡፡
‹‹አይ ብር አለኝ ..ለምን ገዝተን አንበላም…፡፡››
ሁለቱም በደስታ ፈገግ አሉ…‹‹ስንት አለሽ..?››ናኦል ነበር ጠያቂው፡፡
‹‹ጅንስ ሱሪ ኪሷ ውስጥ እጇን ሰደደችና ሁለት መቶ ብር መዛ አወጣች…››
‹‹አይበቃም…››
‹‹አረ ይበቃል..ነይ ዝናሽ ጋር እንሂድ፡፡››
‹‹ዝናሽ ማነች…?››

ከመጽሐፍት መንደር💠

18 Oct, 14:53


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-አስር
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

አዲስአበባ -ኢትዬጵያ
////
ናኦል የእህቱን ድምፅ ከሰማ አራት ቀናት አልፎታል፡፡ይሄ ያልተለመደና ሊታሰብ የማይችል ነገር ነው፡፡እህቱ ቢዚ ብትሆን እንኳን አራት ቀን ሙሉ ቢያንስ ሚሴጅ ትልክለታለች ወይም ኢሜል ትልክለታለች እንጂ እንዲሁ ዝም ልትለው አትችልም፡፡እንዲህ አይነት ነገር አላስለመደችውም፡፡በተለይ የመጨረሻ ጊዜ ስትደውልለት በመጥፎ አየር ፀባይ ወደብራዚል መድረስ አቅቷቸው ያልሆነ ከተማ አርፋ አልጋ ክፍል ሆና ነበር የደወለችለት፡፡የአየር ፀባዩ ከተስተካከለ በማግስቱ ወደብራዚል በረራውን እንደምትቀጥልም ነግራው እሱም አምኗት ነበር፡፡በማግስቱ ትደውልልኛለች ብሎ ጠብቆ ነበር፡፡ማህበራዊ ሚዲያ ላይም ደጋግሞ ሊያገኛት ሞክሯል ፡፡፡ግን ምንም አይነት እንቀስቃሴ የለም፡፡ሚሲጅም ላከላት.. ኢሚልም ደጋግሞ ፃፈላት፡፡መልስ የለም፡፡መስራቤቷ ሄዶ አመለከተ..የሚያውቁት ነገር እንደሌለና ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተፈጥሮ ጥበቃ መስሪያ ቤት ጋር ተፃፅፈው የሚያገኙትን አዲስ መረጃ ከለ ወዲያውኑ እንደሚያሳውቁት ነገረው ሸኑት፡፡የሄደችበትን ድርጅት ድህረ-ገፅ ፈልጎ መረጃ ማሰስ ጀመረ…በአራተኛው ቀን ማታ እቤቱ ቁጭ ብሎ በትካዜ ላይ ሳለ ሰውነት የሚያርድ ልብ የሚያቆም ዜና ከድህረ ገፅ ላይ አነበበ፡፡
‹‹ለተግባራዊ ስልጠና ከፔሩ ወደብራዚል ስትሄድ በአየር ፀባይ መበላሸት ምክንያት ፔሩ ኢኩዩቶስ ከተማ አርፋ የነበረችው ኢትዬጴያዊቷ የተፈጥሮ ጥበቃ ባለሞያ ኑሀሚ በቀለ የገባችበት ጠፋ፡፡ወጣቷ የተፈጥሮ ጥበቃ ኢኬስፐርት አንድ ሆቴል ውስጥ ከአንድ ግለሰብ ጋር አብራ ያደረችና ጥዋትም በታክሲ ተሳፍራ ወደኤርፖርት ጉዞ እንደጀመረች ከሆቴሉ ሰራተኞች ማጣራት ቢቻልም ከዛ በኃላ ግን ኤርፖርት እንዳልደረሰች ታውቋል፡፡ምን አልባትም ወደሀገሯ መመለስ ስላልፈገች እራሷን ሰውራ ሊሆን እንደሚችል የአካባቢው ፖሊሶች ግምታቸውን የተናገሩ ሲሆን ፍለጋው ግን መቀጠሉን ታውቋል›› ይላል፡፡
ጮኸ…ኡ..ኡ ብሎ ጨኸ፡፡ግድግዳው ላይ የተንጠለጠለውን መስታወት በቦክስ ነረተው፡፡መስታወቱ ተፈረካክሶ ወለሉን ሞላው፡፡እጁን ሁለት ቦታ ሸረከተውና በደም ታጠበ…ሰራተኛዋ በርግጋ በውስጥ ልብሷ ብቻ መኝታዋን ለቃ መጥታ ፊቱ እስክትቆም ድርስ እራሱን እንደመሳት አድረጎት ነበር…በሶስት መቶ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ቤታቸው የተኙ ጎሮቤቶች ከእንቅልፋቸው ባነው ግራ እስኪጋቡ ድረስ ነው የጮኸው፡፡
‹‹እህቴ የደሀዋ ኢትዬጵያ ዜጋ ልትሆን ትችላለች..ግን ደግሞ የእኔ እህት ነች…..እኔን ትታ ገነትም ቢሆን መቅረት አትፈልግም…እህቴ አንድ ነገር ሆናለች፡፡እህቴ ታፋናለች፡፡››
‹‹ምንድነው …..ምን ሆነህ ነው…..?ኑሀሚ ምን ሆነች?››ሰራተኛዋ ነች የምትጠይቀው፡፡
‹‹በሄደችበት ሀገር ጠፋች ነው የሚሉት..ሰው እንዴት ዝም ብሎ ይጠፋል….?እህቴን ወንጀለኞች አፍነዋት ነው፡፡››
ከእጁ እየተንጠባጠበ ያለውን ደም በጨርቅ እያሰረችለት‹‹ተረጋጋ እስኪ…የሰው ሀገር አይደለች ያለችው ..ምን አልባት መንገድ ጠፍቷት ያልሆነ ስፍራ ገብታ ያልሆኑ ሰዎች እጅ ወድቃ ሊሆን ይችላል ፡፡››ስትል
…ልታፅናናው ሞከረች፡፡
‹‹አንቺ ደግሞ ከፊቴ ጥፊ …መንገድ የሚጠፋት እንደአንቺ ደንባራ ነገር አደረግሻት እንዴ?፡፡›› አበሳጨችው፡፡
‹‹ያው ማንኛውም ሰው በሰው ሀገር ሲሆን መደናበሩ ይቀራል?››
ከተቀመጠበት ተነሳና ጀኬቱን ከሶፋው ላይ አነሳ …ወደመኝታ ቤቱ ሄደና የመሳቢያውን ኪስ ከፍቶ የሆነ ያህል ብር በማውጣት በኪሱ ጨመረ …ከሌለኛው መሳቢያ ሽጉጥ አወጣና በጀርባው ሽጦ ወጣ ፡፡ሰራተኛዋ ሳሎኑ መሀከል ተገትራ ግራ በመጋባት እየጠበቀችው ነበር፡፡ቀጥታ ወደሳሎኑ በራፍ ሄዶ መክፈት ጀመረ፡፡
‹‹እንዴ ብቻህን በውድቅት ለሊት ወዴት ነው…?በዛ ላይ ቆስለሀል…ልብስ ልልበስና አብሬህ ልምጣ›››አለችው፡፡
‹‹ወዴት ነው የምትመጪው?››
‹‹ወዴት ማለት ምን ማለት ነው…?ለእኔም እኮ እህቴ ነች …ልፈልጋት ነዋ፡፡››
‹‹አሀ ልትፈልጌት ..ደቡብ አሜሪካ?››
‹‹የትስ ቢሆን እንኳን ሰው ከብትም ጠፍቶ ዝም ተብሎ መቀመጥ ይቻላል እንዴ?፡፡››
እንግዲያው ደቡብ አሜሪካ ትንሽ እራቅ ስለሚል ወፈር ያለ ልብስ ልበሺ ደግሞም የእግር መንገድ ስላለው ደህና ጫማ አድርጊ››አላት፡፡
‹‹ደግ…መጣሁ ቆየኝ ››አለችና ተንደርድራ ወደመኝታ ቤቷ ሄደች፡፡ይንን ንግግር በሰላሙ ጊዜ ሰምቶት ቢሆን ኖሮ ሆዱን ይዞ እስኪያመው ይስቅ ነበር፡፡ዛሬ ግን አይችልም፡፡
‹‹አለማወቅ ደጉ ››አለና ሳሎኑን ከፍቶ ወጣና ዘግቶ ቀጥታ ወደውጨኛው የአጥር በራፍ ሔደ..ወለል አድርጎ ከፈተውና ፒካፕ መኪናውን አስነስቶ ግቢውንም አካባቢውን ለቆ ወጣ፡፡
አስራአምስት ደቂቃ ከነዳ በኃላ ስልኩን አንስቶ አንድ አእምሮ ውስጥ በስውር የተቀመጠ ቁጥር አስታወሰና‹‹አስቸኳይ›› ብሎ ፃፈበትና ላከው፡፡እዚህ ቁጥር ላይ ሲፅፍ ከሶስት አመት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜው ነው፡፡የሞትና የሽረት ጉዳይ ካልሆነ እንዳይደውል ተነግሮታል፡፡እና ሁል ጊዜ መደወል ወይም መልዕክት መላክ ይፈልግና ግን ደግሞ የተሰጠውን ማስጠንቀቂያ እንደቀልድ ችላ ማለት ስለማይችል ውጦ ስሜቱን ያዳፍነዋል፡፡ያም ቢሆን ግን ስለጤንነቷና ስለለችበት ሁኔታ በተዘዋዋሪም ቢሆን በየጊዜው ያረጋግጣል፡፡ ግን አሁን ጊዜው ደርሷል…ለእሱ ከእህቱ መጥፋት በበለጠ የህይወት እና የሞት ሽረት ጉዳይ የለም...ለዛ ነው ይሄን መልዕክት በድፍረት የላከላት፡፡
መልዕክቱ የተላከው ምስራቅ የምትባል በእሱም ሆነ በእህቱ ህይወት ላይ ከፍተኛ ድርሻ እና ተፅዕኖ ያላት የደህንነት ሰው ስልክ ላይ ነው፡፡አሁን ካጋጠመው ችግር መፍትሄ ልታስገኝለት የምትችል በምድር ላይ አንድ ትክክለኛ ሰው ብትኖር እሷ ነች፡፡እሷ ከሀገር ውስጥም ሆነ ከአለም አቀፍ የዲፕሎማሲው ማህብረሰብ ጋር ጥብቅ የሆነ ግንኙነት ስላላት የሆነ ነገር ልታደርግለት እንደምትችል እርግጠኛ ነው፡፡
ቀጥታ ወደ እስታዲዬም ነው የነዳው፡፡መስቀል አደባባይ ሲደርስ መኪናውን አቆመና ወደ መቀመጫወቹ በመሄድ ኩርምት ብሎ ተቀመጠ፡፡በዛ በውድቅት ለሊት በሰባት ሰዓት አልፎ አልፎ ውር ውር ከሚሉ መኪኖች ውጭ አካባቢው ጭር እንዳለ ነው፡፡ብርዱ ግን ያንሰፈስፋል፡፡የጃኬቱን ዚፕ አንሸራተተና ወደላይ ቆለፈው፡፡ይሄንን ብርድ እና ስቃይ ያውቀዋል ፡፡ሰውነቱ ውስጥ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ ውስጥም ጭምር ነው ያለው፡፡ በርካታ አመታት በዛ በጮርቃ እድሜው ከአንዲቷና ከተወዳጅ እህቱ ጋር በረንዳ ኖሮ ያውቀዋል፡፡አሁን መልዕክት ልኮላት እስክትመልስለት ድንጋይ ላይ ቁጭ ብሎ በብርድ እየተጠበሰ የሚጠብቃት ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ እንዴት እንዳገኘቻቸው በትዝታ አመታትን ወደኃላ ተመልሷ ማመንዠግ ጀመረ ፡፡የ12 አመት ጮርቃ ታዳጊ እያሉ እንደተለመደው 22 በሚገኝ በረንዳቸው ላይ በተለመደው መልኩ ተኝተው ነበር፡፡ሰዓቱ ልክ አሁን ባለበት ተመሳሳይ ሰዓት ላይ ነው ፡፡ከለሊቱ ሰባት ሰዓት ፡፡እሱና እህቱ እርስ በርስ ተቃቅፈው አሮጌ ብርድልብስና ከላይ ጆንያ ደርበውበት ጋደም ብለው ወጪ ወራጁን በማየት ላይ ነበሩ፡፡
‹‹ምነው ወንድሜ እንቅልፍ እምቢ አለህ እንዴ?››ስትል ኑሀሚ ጠየቀችው፡፡
‹‹አዎ እህቴ…ያቺን ሴትዬ አየሻት?››
‹‹የቷን?››
‹‹ያቺ ከስልክ ፖሉ አጠገብ ያለችው ልጅ፡፡››
ከትከሻዋ ቀና አለችና አየቻት‹‹አዲሷን ልጅ እያልከኝ ነው?››
‹‹አዎ…አዲሷን ልጅ…፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

18 Oct, 14:52


ከ12 አመት የእስር ጊዜያት በኋላ ማምለጥ ቻለና ቤቱ ሲደርስ፤ ሚስቱ፦ "ከ9 ሰአት በፊት ማምለጥህን በቲቪ ስምቻለሁ ፤ እስካሁን የት ነበርክ ደግሞም ምን እያደረክ ነበር?" ብላ ጠየቀችው። እሱም ስልኩን አንስቶ 911 ደወለ ፖሊሶቹን ጠራቸው ከዛ እጁን አሳልፎ ሰጠ 🙂

ከመጽሐፍት መንደር💠

17 Oct, 14:09


አንዱ ጀለስ ነው አሉ…. ከስራ ተባሮ  በተጨናነቀ ሐይገር ተሳፍሮ ወደቤቱ ሲገባ አከራዩ የቤት ኪራይ ብር እንደጨመሩ ነገሩት።

ቀና አለና ወደ ፈጣሪ....
“ይሄንማ መጥቼ ነው ምነግርህ”

ከመጽሐፍት መንደር💠

16 Oct, 18:43


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-ዘጠኝ
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ባለ ኮፍያ ጀኬት አወጣና ሰጣት፡፡በፈገግታ አመሰገነችውና እርምጃዋና ሳታቆም ለበሰች፡፡
ፊት ለፊታቸውም ያሉት እራቅ ብለዋል ኃላም ያሉት ቢያንስ በ20 እርምጃ ወደኃላ ቀርተዋል፡፡፡ስለዚህ በምቾት ታወራው ጀመረ፡፡
‹‹ቁራኛዬ..ስለመልካምነትህ አመሰግናለሁ››አለችው፡፡
‹‹ቁራኛዬ ማለት ምን ማለት ነው?››ጠየቃት፡፡
‹‹በሀገራችን የጥንት ጊዜ ቁራኛዬ የሚባል ባህላዊ የፍርድ ስርዓት ነበር፡፡ በዳይና ተበዳይ፤ሰራቂና ተሰራቂ ፤ገዳይና የተገደለበት ፍርድ የሚሰጥበት ቦታ እስኪደርሱ ድረስ እንዲህ እንደእኔና እንደአንተ በአካባቢው ሽማግሌ ሸማቸውን አንድ ላይ ይቋጥርሩትና እርስ በርስ አቆራኝተው ይልኳቸዋል፡፡በጉዞቸው ታዲያ አንድ ሌላውን በመንከባከብ..ከአደጋ በመጠበቅ ፍርድ እስከሚያገኙበት ቦታ ድረስ በሰላም የመድረስ ግዴታ አለባቸው፡፡ከዛ ተከራክረውና ማስረጃቸውና አቅርበው የተወሰነው ከተወሰነ በኃላ ነገሩ ይደመደማል ፡፡
‹‹የሚገርም ባህል ነው፡፡››
‹‹አዎ ነው..ለመሆኑ ትክክለኛ ስምህ ማን ነው?፡፡››
‹‹ካርሎስ››
‹‹የእኔ ኑሀሚ ነው ..ኢትዬጵያዊ ነኝ፡፡››
‹‹ኢትዬጵያ የት ነች..?ኢስያ አህጉር ውስጥ ነች?››
‹‹አይ አፍሪካ ነች….ምስራቅ አፍሪካ፡፡››
‹‹እ አዎ አስታወስኩ…ታዲያ እዚህ እንዴት ተገኘሽ?››
‹‹በናንተ ተጠለፍኩ እንጂ… የተባበሩት ድርጅት የተፈጥሮ ጥበቃ ፅ/ቤት ባዘጋጀው አለምአቀፍ ሴሚናር ላይ ለመካፈል ነበር አመጣጤ፡፡››
‹‹እ የተፈጥሮ ጥበቃ ላይ ነው የምትሰሪው?››በአድናቆት ጠየቃት፡፡
‹‹አዎ …ነበር፡፡››
‹‹እድለኛ ነሽ…የተፈጥሮ ጥበቃ ወታደር መሆን ከምንም በላይ የሚያኮራ ስራ ነው፡፡በአሁኑ ጊዜ የሰው ልጅ በከፍተኛ ትጋትና ጥረት ምድርን ለማውደም እየሰራ ነው….ያ በጣም አሳሳቢ እና አደገኛ ጉዳይ ነው..ግን ደግሞ ተስፋ እንዳንቆርጥ የሚያደርገን እንደአንቺ አይነት ጀግኖች ያንን ጥፋት ለማክሰም ሲለፉና ሲጥሩ ስለምናይ ነው፡፡ ››
እሷ ለተፈጥሮ ጥበቃና እንክብካቤ እሱ በሚያስበው ልክ ቁርጠኝነቱ ሆነ ፍላጎቱ እንደሌላት ብታውቅም ያንን በግልፅ ልትነግረው አልፈለገችም፡፡ስለእሷ አሁን እየተሰማው ባለው አድናቆትና ክብር እንዲቀጥል ፈልጋለች..ምን አልባት በሆነ አጋጣሚ ሊጠቅማት አንደሚችል አሰበች፡፡
‹‹ተፈጥሮ ላይ ያለህ ፍላጎት ጥልቅ ይመስላል?፡፡››

‹‹አዎ እዚህ በምታይው መልኩ ለመኖሬ ምክንያቴ ለተፈጥሮ ካለኝ ቀናኢነት የተነሳ ነው፡፡ከአማዞን ጫካም ሆነ ከአማዞን ወንዝ ፍቅር ይዞኛል፡፡ይሄው እዚህ ከገባሁ አምስት አመት አለፈኝ…በተቻለኝ አቅምና ዕውቀት የዚህ ደን ውስጠ ሚስጥሩን በርብሬ እያጠናሁ ነው፡፡እስከአሁን ሁለት መፅሀፍ አሳትሜያለሁ….አሁን ደግሞ ሶስተኛውን እየሰራው ነው፡፡››ብሎ አስደመማት፡፡
‹‹የእውነትህን ነው የምታወራኝ?››
‹‹አዎ እውነቴን ነው፡፡››
‹‹እስኪ ስለአማዞን ጥቂት ንገረኝ፡፡››አለችው
‹‹ምን ልንገርሽ…?››
‹‹ስለአጠቃላይና መሰረታዊ ነገሮች፡፡››
 
‹‹እሺ …አማዞን የአለማችን ትልቁ ደን ሲሆን 40 በመቶ በሚሆኑት የደቡብ አሜሪካ ሃገራት ላይ አርፏል፡፡ የአማዞን ጥቅጥቅ ደን 9 ሀገራት ላይ የረፈ በዓለም ላይ ትልቁ ሞቃታማ ደን ሲሆን የሚያካትታቸው ሀገሮችም ብራዚልን  60% ፣ ፔሩ  13% የደን ሽፋን ፣ ኮሎምቢያ 10% እና ቀሪው 17% ቬንዙዌላ ፣ ኢኳዶር ፣ ቦሊቪያ ፣ ጉያና ፣ ሱሪናሜ እና የፈረንሳይ ጓያና የአማዞን ደን የጋራ ባለቤቶች ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የአማዞን ስፋት የህንድን ሁለት እጥፍ ያክላል፡፡ያ ማለት አማዞን አንድ ላይ ተካሎ እራሱን የቻለ አንድ ሀገር ይሁን ቢባል ከ30ሚሊዮን በላይ ዜጎች ያሉት የአለማችን 9ኛው ትልቁ ሃገር ይሆን ነበር ማለት ነው፡፡››
‹‹ይገርማል፡፡››ብላ አድናቆቷን ገለፀችለት፡፡
በዛ ተበረታቶ ማብራሪያውን ቀጠለ‹‹ሌላው በአማዞን ደን ከ350 በላይ ነበር ጎሳዎች በውስጡ ተበታትነው ሲኖሩበት ከእነዛ ጎሳዎች መካከል ከ75 በላይ የሚሆኑት ጎሳዎች እርስ በእርስ ተገናኝተው የማያውቁ እራሳቸውን ከሌላው ማህበረሰብ፤ከመንግስትም ሆነ ከማንኛውም ቴክኖሎጂ ያራቁ ናቸው፡፡ ስለእንስሳቱ ንገረኝ ካልሺኝ ደግሞ አማዞን በአለማችን ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው አጥቢ አንስሳት፤አዕዋፋት እና በደረት የሚሳቡ ፍጡራን የሚገኙበት ደን ነው፡፡በዛ ጥቅጥቅ ደን 400 ቢሊዮን ዛፎች፤40 ሺህ የእጽዋት እና 1300 የአዕዋፍ ዝርያዎች በውስጡ ይገኛሉ፡፡››
በገለፃው የእውነት ከልቧ ተደምማበት‹‹እውነትም ከዚህ ደን ጥልቅ የሆነ ፍቅር ይዞሀል››የሚል አስተያየት ሰጠችው፡፡
‹‹አዎ…በትክክል ገልጸሸዋል፡፡››

ከመጽሐፍት መንደር💠

14 Oct, 19:02


እርግጥ እሷም ከእሱ ጋር ተቀራራቢ የሆነ ሀሳብ ሁሌ በውስጧ ታሰላስል ነበር፡፡ስታድግ የተወለዱበትንና ያደጉበትን የወላጆቾን ቤት መልሳ መግዛት የዘወትር ምኞቷ ነበር፡፡አዎ በወቅቱ እቤቱን የአባታቸው የልብ ጓደኛው በነበረ ሰው ባለቤትነት ተይዟል፡፡ ወላጆቻቸው ሞተው ወር እንኳን ሳይሞላው ነበር ከመሟቱ በፊት ለስራ ብሎ ብዙ ሚሊዬን ብር ተበድሮኛል ብሎ የተናገረው፡፡ብዙም ሳይቆይ የተናገረውን የሚያረጋግጥለት ሰንድ አቀረበ፡፡ከዛ በቀላሉ በፍርድ ቤት ከሶ ወላጆቻቸው ሞተው በተቀበሩ በሶስተኛው ወር እቤቱን ተረክበ፡፡ለእነሱ ቀርቦ የሚከራከርላቸውም ሆነ ወስዶ የሚያሳድጋቸው አንድም ዘመድ መቅረብ ስላልቻለ …ሰውዬው ጎዳና ጣላቸው የሚለውን የሰው አፍ ብቻ በመፍራት ወስዶ ለማደጎ ቤት አስረከባቸው፡፡ኑሀሚ በዛ ጮርቃ እድሜዋ ላይ ሆና እንኳን ያ ሁሉ የተወሳሰበ ቲያትር መሰል አሻጥር ፈፅሞ አይዋጥላትም ነበር፡፡ያንን ቤት በጣም ትወደዋለች፡፡ልጅነቷ ያለው እዛ ቤት ውስጥ ነው፡፡ሳቅና ደስታዋ እዛ ቤት የሆነ ቁምሳጥን ወይም የኮመዲኖ ኪስ ውስጥ የተቆመለፈበት ነበር የሚመስላት፡፡እና አንድ ቀን ተሳክቶላት ያንን ቤት ማስመለስና የራሳቸው ማድረግ ብትችል እናትና አባቷንም በከፊልም ቢሆን ከሞት አለም ማስመለስ እንደሆነ አድርጋ ነበር የምትቆጥረው ፡፡ዘወትር ትንሽ በከፋት ቁጥር የሚተኙበትን መኝታ ቤት ትዝ ይላታል፤እናቷ ምግብ የምታበስልበት ኪችን ሙሉ ስዕሉ በአእምሮዋ ይመላለስባት ነበር፡፡አባቷ በእረፍት ቀኑ ቢጃማ ለብሶ በረንዳ ላይ ቁጭ ብሎ መፅሀፍ ሲያነብ …እሷ ድክ ድክ እያለች ከሳሎን መጥታ ታፋው ላይ በመቀመጥ ከኪሱ ስልኩን አውጥታ ጌም ስትጫወት…. ‹‹ናሆሚ እስኪ ድምፁን ቀንሺ ላንብብበት..›› እያለ ሲቆጣት ሁሌ ነበር ድምጹ የሚሰማት……አዎ ስለዛ ቤት ብዙ ብዙ ነገር ትዝ ይላታል፡፡ትዝታ ደግሞ የሰው ልጅ ትልቁ ሀብቱ ነው፡፡የሰው ልጅ ህልውናው የሚረጋገጠው እኮ በሚታየው ስጋና አጥንቱ ብቻ አይደለም…በእስትንፋሱም አይደለም፤እነሱ ለብቻቸው ልክ እንደአንድ እንስሳ እንጂ እንደሰው እንዲታይ አያደርጉትም፡፡ዋናው ሰው መሆንን የሚያጎናፅፈን ያለፈ ህይወታችንን በትዝታ ቋት በማከማቸትና በምናብ መንኮራኩር ጊዜና ቦታ ሳይገድበን ወደነገ በመመንጠቅ ችሎታችን ነው፡፡ አንድ ሰው ትዝታው ከተደመሰሰና በምናብ ወደነገ የመጓዝ ችሎታው ከተዳከመ ምን እንደሚሆን አስብቱ..በቃ የለም ማለት እኮ ነው፡፡ኢከሌ በቁም ሞቷል ሚባለው እኮ እንደዚህ አይነት ጉዳይ ሲያጋጥመው ነው፡፡ትዝታው ሲዛባበትና ምናብ ሲከስምበት፡፡
በዛን የመከራ ጊዜቸው አንዳንዴ ወንድሟን ለምና ወደድሮ ሰፈራቸው ይዛው ትሄድና በሩቅ ሆነው ግቢውን ይዞሩት ነበር፡፡በስተመጨረሻ ግን በቁጭት ቆስለውና በንዴት በግነው እየተላቀሱ እና አንደኛው ሌላውን እያፅናኑ ሰፈሩን ለቀው ይመለሳሉ፡፡
ናኦል እሷ እያስገደደችው እንጂ እዛ ሰፈር መሄድ አይወድም ነበር፡፡ጭራሽ ስለእዛ ቤትም ማሰብ አይፈልግም….፡፡እሱ ያንን ቤት ወደፊት መልሼ ገዝቼ የእኛ አደረግዋለሁ የሚል ምኞት አልነበረም ያለው፡፡የእሱ እቅድ አንድ ቀን እንደምንም ሁለት- ሶስት ፈንጅ አግኝቼ ውስጡ እስከአሉት ሰዎች ማፈንዳትና አመድ ማድረግ በቻልኩ ብሎ ነበር የሚያስበው፡፡ስለቤታቸው ሲያስብ እልክ ፣ንዴትና የመዘረፍ ስሜት ነበር የሚያሰቃየው፡፡የተዘረፉት ንብረት ብቻ እንዳልሆነ ያውቃል፡፡እናትና አባታቸውንም ጭምር ተዘርፈዋል፡፡ ነገሩን ከእህቱ ጋ አንስቶ አያውራበት እንጂ የወላጆቹ ሞት ላይም ከፍተኛ ጥርጣሬ አለው፡፡ እራሳቸውን አጠፉ ነው የተባለው፡፡የገዛ መኝታቸው ላይ ማታ በተኙበት ጥዋት ደርቀው ነው የተገኙት ፡፡ከመጠን በላይ መድሀኒት በመውሰድዳቸው ለመሞታቸው ዋናው ምክንያት እንደሆነ በሀኪም ተረጋግጧል፡፡እርግጥ የዛን ሰሞን ጉንፋን መሰል በሽታ እንደወረርሺኝ ገብቶና እነሱም ታመው  ስለነበረ…በተከታታይ  የሚወስዱት  መድሀኒት  ነበር፡፡ግን  እንዴት  ለሞት እስኪዳርጋቸው ድረስ ከመጠን በላይ መድሀኒቱን ሊወስዱ ቻሉ…?ይሄ ናኦልን ብቻ ሳይሆን ብዙ ትላልቅ ሰዎች የማይመስል ነገር ነው ሲሉ ሰምቷል፡፡
ከወላጆቹ ግድያ ጀርባ ያለውን እውነት ለማጣራት ከፍተኛ ፍላጎት አለው፡፡ያንን ለማድረግ ደግሞ ኃይል ያለው፤ የተናገረው የሚደመጥለት፤ ያዘዘው የሚከወንለት፤ ቆፍጠን ያለ ሰው መሆን እንዳለበት ቀድሞ ነበር እየገባው ፡፡ኃይል ከስልጣን ወይ ከገንዘብ ነው የሚገኘው፡፡ያንን የጎዳና ህይወት ባሳለፋቸው ጊዜያቶች የተማረውና የገባው ነገር ነበር፡፡ለዛ ነው በወቅቱ ለገንዘብ ከፍተኛ ፍቅርና ፍላጎት ያደረበት፡፡
‹‹እህቴ ስሚኝ…እንማራለን፡፡ደግሞ እንዳልኩሽ ባንማርም በሆነ መንገድ ብቻ ሀብታም መሆን አለብን፡፡ግን ዋናው ሁሌ አብረን መሆናችን ነው ፡፡ መተሳሰብና መረዳዳት አለብን፡፡ሁለታችን ከተጋገዝን ያልኩሽን እናሳካለን፡፡›› ነበር ያላት
‹‹እሺ እንዳልክ፡፡››አለችና በድጋሚ ተንጠራርታ ጉንጮን ሳመችው፡፡ ..የሰጣትን ቸኮሌት ሽፋን ላጠችና ግማሹን ቆርሳ አቀበለችው፡፡
‹‹ኸረ እኔ ጣፋጭ እንደማልወድ አታውቂም፡፡ብስኩቱን ነው የምበላው፡፡›› በማለት የብስኩቱን ላስቲክ በጥርሶች መካከል አስገብቶ መቅደድ ጀመረ፡፡

‹‹ወንድሜ ደግሞ …ቸኮሌት አሁን እምቢ ይባላል?››

ከመጽሐፍት መንደር💠

14 Oct, 19:02


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-ስምንት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ጥያቄዋ እሱን በጣም ነበረ ያሳቀቀው ፤ ወዲያው ነበር ከተቀመጠበት ተስፈንጥሮ በመነሳት ወደእሷ የተጠጋው፡፡ከዛ ከጎኗ ተቀመጠና ወደራሱ ስቦ አቀፋት..በዛ ልስልስና ጣፋጭ አንደበቱ‹‹እንደውም በጣም የምወድሽማ አሁን ነው፡፡በጣም እኮ ነው የምታሳዝኚኝ፡፡አንቺ ብቻ ነሽ እኮ ያለሺን፡፡እንዴት አንቺን ላለመወደድ እችላለሁ?ከአንቺ ውጭ እኮ ምንም ነገር የለኝም፡፡››ብሎ በመረረና በጠነከረ ንግግር ስለፍቅሩ ጥልቀት አስረዳት፡፡
በጣም ነበር ያሳዘናት‹‹አንተም እነአባቢን ተከትለህ ጥለኸኝ ሄደህ ቢሆን ኖሮ ምን አሆን ነበር….?››አለችው ፡፡ያንን ስትለው መላ ሰውነቷ በፍራቻ እየተንቀጠቀጠባት እንደነበረ ትዝ ይላታል፡፡ናኦል ከገቡበት ከጨላማ ውስጥ ከሚመዘዝ የትዝታ ጉዞ በከፊልም ቢሆን እንዲወጡ ፈለገና የጫወታቸውን ርዕስ ቀየረ፡፡‹‹በቃ አሁን ልደሽን እናክብር….››አላት
‹‹ልደቱ የእኔ ብቻ ነው እንዴ…?የሁለታችንም እኮ ነው፡፡››
‹‹ታውቂያለሽ እኔ ልደቴን ማክበር እንደማልወድ››
‹‹እንዳልክ እሺ… ግን መጀመሪያ የእኔን ሻማ እንለኩስና የእነአባቢን የሙት አመት መታሰቢያ እናክብር››ብላ መለሰችለት፡፡
እሱ  ግን‹‹አይ  ልደቱም  ሀዘኑም  የእኛው  አይደል  ..ሁለቱንም  ሻማዎች  አንድ  ላይ እንለኩሳቸው››አላት
አልተከራከረችውም‹‹ ክብሪቱን የት አደረከው?››

ከኪሱ ውስጥ ፈልጎ አወጣና ሰጣት ..ጫረችና የመጀመሪያውን የራሷን ሻማ በመለኮስ አባቷ መቃብር ላይ በማንጠባጠብ እረሱን ችሎ እንዲቆም አደረገች፡፡ከዛ ሌለናውን ሻማ ከወንድሟ እጅ ተቀበለችና ለኩሳ ወደግራዋ ዞራ እናቷ መቃብር ላይ በተመሳሳይ መልኩ አስቀመጠች፡፡በመቀጠል የራሷን የተቀዳደደ የጃኬት ኪስ ፈተሸችና ሁለት ብስኩት አወጣች፡፡ወደወንድሟ   በስስት   እያየች‹‹ወንድሜ   ለልደቴ   ሻማ   ስለለኮስክልኝ አመሰግናለው .. ለእንተም መልካም ልደት ይሁንልህ..ለእኔ ስትል አብረኸኝ ስለተወለድክ አመሰግናለው፡፡››አለችውና ከኪሷ ያወጣችውን ብስኩት  እጁ ላይ አደረገች፡፡
ትዝ ይላታል በጣም ነበር ደስ ያለው፡፡ያንን ብስኩት መያዟን አያውቅም ነበር፡፡ሳንቲሙን ከየት አግኝታ? መቼ ገዝታ? እንዴት ከእሱ ደብቃ ይዛ እንደመጣች አያውቅም፡፡እሱም ግን ሊያስደምማት ለሳምንት ሲያስብበት ነበረ፡፡እጁን ወደኪሱ ሰደደና አንድ ቸኮሌትና አንድ ጦር ማስቲካ በማውጣት .‹‹እህቴ እንኳን ተወለድሽ..ደግሞ ልደቱን የሚያከብር ሰው ስጦታ ይቀበላል እንጂ ስጦታ አይሰጥም›› ብሎ እጆ ላይ አስቀመጠላት፡፡
ኑሀሚ ቸኮሌትና መስቲካውን በጣም እንደምትወደው ያውቃል፡፡ ወላጆቻቸው በህይወት እያሉ እናትዬው የመስቲካ ሱሰኛ አባትዬው ደግሞ የቸኮሌት ሱሰኛ አድርገዋት ነበር፡፡ያኔ በሰላሙ ጊዜ በቀን ሁለቴ ወይም ሶስቴ ሰበብ እየፈጠረች ታለቅስ ነበር፡፡ለቅሶዋን ምታቆመው ደግሞ ወይ ቸኮሌት ወይም ደግሞ መስቲካ ሲሰጣት ብቻ ነበር፡፡ይሄም በደንብ ስለሚታወቅ ቀደም ተብሎ ይገዛና ተደብቆ ይቀመጥላታል፡፡ …..እና በወቅቱ የወንድሟ ስጦታ እናትና አባቷን በአንድ ላይ በጥልቀት እንድታስታውስ ነበር ያደረጋት፡፡ መልካቸው ብቻ ሳይሆን ጠረናቸውም ነበር ትዝ ያላት፡፡
‹‹ወንድሜ በጣም ነው ያስደሰትከኝ፡፡አንተ ስላለህልኝ በጣም እድለኛ ነኝ፡፡›› አለችው፡፡
‹‹እህቴ ስናድግ የቸኮሌት ፋብሪካ ይኖረኛል፡፡እና ያንን ፋብሪካ ላንቺ ስል ነው የምከፍተው፡፡ሁል ጊዜ የፈለግሽውን ያህል ቸኮሌት መብላት እንድትቺይ እፈልጋለሁ፡፡››ሲል ከጥልቅ ልቡ የመነጨውን ምኞቱን በፍቅር እና በስስት አይን አይኗን እያየ ነበር ቃል የገባላት፡፡ወደእዚህ አሁን ወዳለችበት ደቡብ አሜሪካ ከመምጣቷ በፊት ወንድሞ የዛን ጊዜ በልጅነታቸው ቃል የገባላትን ቸኮሌት ፋብሪካ ለመገንባት ማሽኑ የሚተከልበትን ዌርሀውስ ማስገንባት ጀምሮ ነበር፡፡ምን አልባት እስከአሁን አጠናቆትም ሊሆን ይችላል፡፡በጣም የሚያሳዝነውና መራሩ ሀቅ ግን ቸኮሌት ፋብሪካው ተተክሎ ማምረት ቢጀምር እንኳን እህቱን ማብላት አይችልም፡፡እህቱን በሰው ሀገር ምድር ላይ በሞት መነጠቋን ካወቀ ፋብሪካውን ያቃጥለዋል፡፡በዛ እርግጠኛ ነች፡፡
በወቅቱ በዛ የልጅነት ጊዜያቸው በወላጆቻቸው መቃብር ስር ስለቸኮሌት ፋብሪካው ቃል ሲገበላት‹‹ወንድሜ ቸኮሌት ፋብሪካ ለመክፈት እኮ ብዙ ብር ነው የሚያስፈልገው…ሀብታም መሆን አለብህ..ያ እንዴት ሊሆን ይችላል? ፡፡››ብላ ነበር የጠየቀችው፡፡
ወንድሟ እጆቹን ዘርግቶ ግራና ቀኝ ትከሻዋን በመያዝ ትኩር ብሎ አይኖቹን አይኖቾ ላይ ተክሎ‹‹አዎ ሀብታም መሆን አለብኝ፡፡እኔ ብቻ ሳልሆን አንቺም ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡ለእኛ ሀብታም መሆን የግድ ነው፡፡እኔ ላንቺ ስል ሀብታምና ብዙ ብር ያለው ሰው መሆን እፈልጋለሁ፡፡አንቺም ለእኔ ስትይ እንደዛው ሀብታም መሆን አለብሽ፡፡››ነበር ያላት
‹‹እንዴት ግን..?ትምህርታችንን ከሶስተኛ ክፍል እንዳቋረጥን ነው፡፡ሳንማር እንዴት ነው ሀብታም ልንሆን የምንችለው?››
‹‹እንችላለን፡፡ማለቴ ሳይማሩ ሀብታም መሆን የሚቻል ይመስለኛል፡፡ያለበለዚያ ቡዙ የተማሩ ሆነው ምንም ብር የሌለቸውና አንዳንድ ያልተማሩ ሰዎች ደግሞ ሀብታሞች ሆነው አናገኝም ነበር፡፡አዎ እንዴት እንደሆነ ለጊዜው ባላውቅም ሳይማሩም ሀብታም መሆን እንደሚቻል እርግጠኛ ነኝ፡፡››አላት፡፡
አዎ..የወደፊት ህልማቸውን በተመለከተ ወንድሟ የሚያወራው ነገር በጣም መሳጭ እና አጓጊ ሆኖ ነበር ያገኘችው፡፡ቢሆንም ግን እንዴት ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል በወቅቱ ምንም  ፍንጭ  አልታያትም፡፡ግን  ደግሞ  የወንድሟን  ንግግር  የሞኝ  ቅዠት  አድርጋም አልወሰደችውም፡፡ ወንድሟን አይደለም በዛን ጊዜ አሁንም ታምነዋለች፡፡ከፍቅር የመነጨ እምነት፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

12 Oct, 18:15


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-ሰባት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ፔሩ/አማዞን ወንዝ
ዳግላስን ከኑሀሚ ነጥለው በአማዞን ወንዝ ላይ የተወሰነ ይዘውት ከተጓዙ በኃላ ሌላ እጅግ በጣም የተቀናጣ ግን ደግሞ መለስተኛ ዘመናዊ ጀልባ አጠገብ አቆሙና አሸጋገሩት፡፡ምንም እየገባው ነገር ባይኖርም ግን ደግሞ መከራከርና መጨቃጨቅ ባለመፈለጉ እንዳደረጉት እየሆነላቸው ነው፡፡ልክ ከትንሿ ጀልባ ወደቅንጡ ውሀና ዘመናዊው ጀልባ አሸጋግረውት ገና ወለሉ ላይ እንዳረፈ..አንድ ሀያዎቹ መጀመሪያ ላይ የምትገኝ ፤ደማቅ ጥቁር ፀጉሯ መቀመጫዋ ላይ የደረሰ ፤መልኳ ጉርድርድ ያለ ግን ደግሞ ሳቢ የሚባል የደም ግባት ያላት ሴት ከውስጥ ወጣችና ተንደርድራ መጥታ ተጠመጠመችበት፡፡ግራ ገባው፡፡ብዥም አለበት፡፡ይህችን ሰውነቱ ላይ ተጠምጥማ በእንባ በመታጀብ እየሳመችው ያለችውን ልጅ የሆነ ቦታ የሆነ ጊዜ ያውቃታል..አዎ በአእምሮ ብልጭ ድርግም እያለችበት ነው ..ግን የት እና እንዴት እንደሚያውቃት ምንም ትዝ ያለው ነገር የለም፡፡
‹‹ቤብ..ሰላም ነህ…?ወይኔ በኢየሱስ……ምንም አልሆንክም…?›› መላ እሱነቱን እየተሸከረከረች እያች  ግንባሩን ጉንጮቹን እጆቹን እያፈራረቀችና እያገለባበጠች ትሰመው ጀመር፡፡ በዙሪያቸው ያሉ ወጠምሻና አብረቅራቂ መሳሪያ የታጠቁ ሰዎች አንገታቸውን አቀርቅረው ዙሪያቸውን ከበው እየሆነ ያለውን በቆረጣ እየተመለከቱ ናቸው፡፡ልጅቷ እየጎተተች ወደውስጥ ይዛው ገባች ፡፡ደረጃውን እየወረዱ ወደውስጠኛው መኝታ ክፍል ይዛው ገባች፡፡ ሰፊውን ክፍል አልፋ እልጋ ወደ ተነጠፈበት መለሰተኛ ክፍል ይዛው ገባቸው፡፡ባለመሳሪያዎቹ ባሉበት በረንዳ እንደቀሩ ናቸው፡፡
ዳግላስ በገባበት የቅንጡ ጀልባዋ መኝታ ቤት ውስጥ የምታምር ድንብሽብሽ ያለች በግምት ሶስት ወይም አራት አመት የሚሆናት ጥቁር ሉጫ ፀጉሯ ግንባሯ ላይ ድፍት ብሎ ግማሽ ፊቷን የሸፈናት ልጅ ጭልጥ ያለ የሰላም እንቅልፍ ውስጥ ገብታለች፡፡ህፃኗን በትኩረት ሲያያት የሆነ ብዙ ቀለማቶች በአእምሮው ብልጭ ድርግም ብልጭ ድርግም እያሉ ይረብሹት ጀመረ፡፡በፀጥታ አልጋው ጠርዝ ላይ ተቀመጠና ቀኝ እጁን ወደ ልጅቷ ልኮ በቀስታ ግንባሯ ላይ የተደፋውን ፀጉሯን ከግንባሯ ላይ እያነሳ ትራሱ ላይ አስተኛው..እናትዬዋ ስሩ በፀጥታ ቆማ የሚያደርገውን እየተመለከተች ነው፡፡አሁን ሙሉ በሙሉ የልጅቷ ገፅታ ይታያል፡፡ይህቺ ልጅ ልብ ውስጥ ብቻ ሳይሆን ነፍሱ ውስጥም እንዳለች እርግጠኛ ነው፡፡ይሄንን የተረዳው ደመነፍሳዊ በሆነ ስሜቱ ነው፡፡በትክክለኛው ግን ምንም ትዝ እያለው ያለ ነገር የለም፡፡
አንገቱን ቀና አደረገና ጎኑ የቆመችውን አማላይ ሴት ተመለከታት‹‹የምታግዢኝ ነገር የለም?››ሲል ጠየቃት፡፡
የሚፈልገውን ሁሉ ለማድረግ ሙሉ ፍቃደኛ እንደሆነች በሚያረጋግጥ ንግግር ‹‹ምን ላድርግልህ የእኔ ፍቅር? የፈለከውን ጠይቀኝ››አለችው፡፡
‹‹አሞኛል ..በፊት የምወስዳው መድሀኒት ወይም ኪኒን ነገር ይኖራል?፡፡››
ደነገጠች….የእሷን   መደንገጥ  ተከትሎ  እሱም  ደነገጠምም  ግራ ተጋባምም‹‹ዛሬ መድሀኒትህን አልወሰድክም እንዴ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹እስከማስታውሰው ድረስ ለበርካታ ቀናት ምንም አይነት መድሀኒት የወሰድኩ አይመስለኝም፡፡››
‹‹ይሄ የፓብሎ ተግባር ነበር፡፡ግን እሱ ራሱ የት እንደገባ ምንም የሚታያውቅ ነገር የለም፡፡ቆይ መጣሁ›› ብላ ሔደችና ከሁለት ደቂቃ በኃላ ሁለት ኪኒኒ ከእሽግ ውሀ ጋር ይዛ መጣች፡፡ኪኒኖቹን ከእሽጉ ፈልቅቃ አቀበለችው….‹‹ውሀውን ከፈተችና በል ዋጥና ለአንድ ሰዓት ያህል ጋደም በል… ስትነሳ ሰላም ትሆናለህ….››
‹‹አልገባሽም ..አመመኝ ስልሽ እኮ ህመም አይደለም..ምንም የማስታውሰው ነገር የለም እያልኩሽ ነው..አንቺን ጭምር ማንንም አላስታውስም››የተረዳችው ስላልመሰለው ፍርጥ አድርጎ እውነቱን ነገራት፡፡
‹‹ገባኝ የእኔ ፍቅር ..ሁሉ ነገር ይስተካከላል… ብቻ ያልኩህን አድርግ… መድሀኒቱን ዋጥና ከልጅህ ጎን ተኛ፡፡››እንዳለችው መድሀኒቱን ተቀበላትና ዋጠ፡፡ጫማውን አወለቀና ቀስ ብሎ አልጋው ላይ ወጣና ከልጁ ጎን ተኛ፡፡ፊት ለፊት ካለው የልብስ ማስቀመጫ ሳጥን ውስጥ አልጋ ልብስ አወጣችና አለበሰችው፡፡ ቀስ ብላ ክፍሉን ዘግታለት ወጣችና ከጠባቂዎቹ ራቅ ብላ የጀልባዋ በረንዳ ላይ ባላ ወንበር ተቀምጣ ከወንዙ ባሻገር ያለውን ጥቅጥቅ የአማዞን ደን በተመስጦ መመልከቷን ቀጠለች፡፡

ምዕራፍ-ስድስት
ኮሎምቢያ/አማዞን ደን ወስጥ
ኑሀሚ ያለችበት ጎጆ የተወታተፈ በራፍ ሲከፈት ሰማችና የጨፈነ አይኗን ከፈተች፡፡ከአጋቾቾ መካከል አንድ ነው፡፡፡አሁን እጆ ላይ ተጣብቆ ከወዲህ ወዲያ በተንቀሳቀሰች ቁጥር ቅጭልቅል እያለ የሚረብሻትን ሰንሰለት ተቆራኝቷት የነበረው ልጅ ነው፡፡በእጁ የሚበላ ነገር በሰሀን እና የሚጠጣ ውሀ በላስቲክ ኩባያ ይዞል፡፡ወደእሷ ተጠጋና በርከክ ብሎ ምግብን አስጠግቶ አስቀመጠላትና የስፓንሽ ቋንቋ ዘየ በተጫነው ግን ደግሞ ባልተደነቃቀፈ እንግሊዘኛ፡፡‹‹ተነሽ ይሄን ምግብ ብይ…ከጥቂት ጊዜ በኃላ በእግር ረጅም መንገድ መጓዛችንን ስለምንቀጥል ጥንካሬው ያስፈልግሻል፡፡››አላት፡፡
ጎኑ ላይ የያዘውን አብረቅራቂ ኮልት ሽጉጥ በጎሪጥ እየተመለከተች‹‹ወደየት ነው የምትወስዱኝ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹እሱን ለአንቺ ለመናገር ፍቃዱ የለኝም፡፡››ሲል መለሰላት፡፡
‹‹እባክህ…እህት የለህም..እኔ እኮ በጣም ከሩቅ አህጉር የመጣው ምስኪን ወጣት ነኝ…ምን ላደርግላችሁ ነው እንዲህ ከእኔ ጋር የምትሰቃዩት?››አሳዛኝ መስላ ለመቅረብ ሞከረች፡፡
‹‹እህት አለኝ ….ግን ላደርግልሽ የምችለው ነገር ቢኖር  አንድ ምክር ላንቺ መስጠት ብቻ ነው፡፡››
‹‹ምንድነው? እባክ ንገረኝ፡፡››
‹‹ፈፅሞ የሞኝ ስራ እንዳትሰሪ…››
ያልጠበቀችው የምክር አይነት ስለነበር‹‹ምን ማለት ነው?››በማለት ጠየቀችው፡፡

‹‹ጥዋት በምንጓዝበት ጊዜ በየመሀከሉ ሁኔታሽን ስከታተለው ነበር… ለማምለጥ ወይም ለመፋለም የመፈለግ አዝማሚያ አይቼብሻለው፡፡ በእርግጠኝነት ትንሽ እንቅስቃሴ ወይም ሙከራ ካደረግሽ ከመሀከላችን አንድ ወዲያው ነው የሚደፋሽ… እመኚኝ ሌሎቹ እንደእኔ ልስልስ እና ደካማ ነገር አይደሉም፡፡ከፍተኛ ወታደራዊ ስልጠና ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ ጭካኔም ያላቸውና ሰውን በመግደልና ድመት በመግደል መካለከል ምንም ልዩነት የማይታያቸው ገዳዬች ናቸው..እንደውም አጋነንከው ከላልሺኝ ለእነሱ ወሲብ ማድረግና ሰውን መግደል ተመሳሳይ አይነት እርካታ ነው የሚያጎናፅፋቸው፡፡››ሲል መስማት ከምትፈለገው ተቃራኒ የሆነ አስቀያሚ ዜና ነገራት፡፡
‹‹እና መጨረሻዬን ምንም ሳላውቅ ልክ እንደፋሲካ በግ ዝም ብዬ ልነዳ ?››
‹እኔ እንግዲህ እንደዛ የሚሻል ይመስለኛል፡፡በህይወት ነገ ተነገ ወዲያ ምን እንደሚከሰት አይታወቅም፡፡ነገ ይዛ የምትመጣውን እድል ለመጠቅ ደግሞ ዛሬ በህይወት ቆይቶ ነገ ላይ መገኘት ያስፈልጋል፡፡በይ እንዳልኩሽ የቀረበልሽን ብይ…  የእግር ኮቴ እየተሰማኝ ነው፡፡
‹‹ልሂድ››ብሎ ቁጢጥ ካለበት ምንጭቅ ብሎ ተነሳና በራፉን ከፍቶ እንደአመጣጡ ተመልሶ ሄደ፡፡

ከመጽሐፍት መንደር💠

12 Oct, 18:06


Imagine ለመርሳት የታደልን ባንሆን ኖሮስ?!

ከመጽሐፍት መንደር💠

10 Oct, 17:37


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-ስድስት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ

ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ:
ፔሩና/ኮሎምቢ ድንበር
በአለም ላይ በውሀ ከተከበብት ከተሞች መካከል ግዙፍ የሆነችውንና እስከ 200 ሺ ህዝብ በላይ ከሚኖርባትን የኢኩኢቶስ ከተማ ነጥቀው በአማዞን ወንዝ ላይ እያንሳፈፉ አርቀው ወሰዷትና አማዞን ደን ውስጥ ከተቷት።ከጀልባው ወርዳ መሬት ላይ ስታርፍ ይዛዋት የመጡት አራት ሰዎች በመጡበት ጀልባ ወደኃላ ሲመለሱ …መሬት ላይ ቆመው ሲጠብቋት የነበሩ ከነዛኞቹ በላይ አስፈሪ የሆኑ በቁጥር 9 አካባቢ ሰዎች ነበሩ የተቀበሏት፡፡‹‹በዚህ ሁሉ ትጥቅና አጀብ የሚቀበሉኝ ማነች ብለው ነገሯቸው ይሆን?›› ስትል በውስጧ አልጎመጎች፡፡አራቱ ከኃላዋ አራቱ ደግሞ ከፊት አንዱ ከመሀከላቸው በአቋሙ ቀጠን የሚል በአለባበሱ ስርአት ያለውና ..ለስላሳ ቢጤ የሆነ ሰው ወደእሷ ቀረበና እራሱን ከእሷ ጋር አንድ ሜትር ርዝመት ባለው ቀለል ባለ ሰንሰለት በማቆራኘት ከኃላዋ ሆኖ መራመድ ጀመረ፡፡አሁን እሷን በመሀከል አድርገው አማዞን ደን ውስጥ ልክ እንደጉንዳን ሰራዊት ሰልፍ ገብተው ይዘዋት እየተጓዙ ነው።በደን ውስጥ እየተጓዙበት ያለው መንገድ እጅግ ቀጭንና ግራና ቀኝ በተቆላለፉ ሀረጎችና የዛፍ ቅርንጫፎች የተጠላለፈ ስለሆነ አስቸጋሪና በተለይ ለእሷ አስፈሪ ነበር።
በህይወቷ እሷ እራሱ እስኪገርማት ድረስ ከህፃንነቷ የጓዳና ላይ ኑሮዋ ጀምሮ እጅግ አስቸጋሪ አስፈሪና በአደጋ የታጠሩ ብዙ ቀናቶችንና ወራቶችን አሳልፍለች፡፡ወደፊትም ህይወቷ ከአደጋ የፀዳና ከችግር የራቀ እንደማይሆን ታውቃለች፡፡ግን መቼም ቢሆን በአማዞን ጥቅጥቅ ደን ውስጥ ደም የጠማቸው እንደሆነ በሚያስታውቁ ወጠምሻ ጋንግስተሮች እንደከብት እየተነዳች ወደማታውቀው ስፍራ እንደምትወሰድ ፈፅሞ በስህተት እንኳን አስባው አታውቅም ነበር፡፡በዛም ምክንያት አሁን እራሷን ለማዳን ምን ማድረግ እንዳለባት እንኳን ምንም አይነት ሀሰብም ሆነ ዕቅድ ወደ አእምሮዋ እየመጣላት አይደለም። ባላት ወታደራዊ ስልጠና እና የመስክ ላይ ተሞክሮ እየነዷት ካሉት የተወሱንትን ቆልፋ የተወሰኑትን ሰባብራ ልታመልጣቸው ትችል ይሆናል።ከዛስ...?ከዚህ ደን እንዴት ትወጣለች...? የጫካው ነገስታት የሆኑትን አደገኛ አውሬዎችን እንዴት ተፍልማ እንዴት ታሸንፋቸዋለች? በህይወት ጉዞዋ ከሰው ጋር እንዴት መፋለም አንዳለባት እንጂ በጥቅጥቅ ደን ውስጥ ከሚኖሩ ድንብር አውሬዎች ጋር እንዴት መፋለም እንዳለባት የወሰደችው ምንም አይነት ስልጣናም ሆነ የህይወት ተሞክሮ የላትም፡፡ስለዚህ በአደገኛ እንሸላሊት ተነድፍ መንገድ ብትቀርስ..?መርዛም እንቁራሪት ቢነድፏትስ?ከአማዞን ወንዝ ዘሎ የወጣ አዞ በመጋዝ ጥርሶቹ ቢዘነጣጥላትስ? ይሄንና የመሳሰሉትን መአት አስከፊ ሊገጥሙ የሚችሉ ከፊቷ ያሉ መከራዎች አሰበችና አጋቾቻን ለመተናኮል ያላትን ምኞት ለጊዜውም ቢሆን ተወችው፡፡እናም ደግሞ ስለዳግላስ አሰበች…‹‹ይሄኔ እንዴት ሆኖ ይሆን?"
ግራ የተጋባ ማንነቱና ለእሷ የነበረው ደግነት ትዝ አላት፡፡ጥዋት የሠጣትን የ20 ሺ ዶላር ስጦታ አስታወሰች ..ልብሷን የያዘ ሻንጣዋን ከኃላ ካሉት አጓቾቾ መካከል አንዱ ይዞታል፡፡ብሩንና ፓስፖርቶ ያለበትን የእጅ ቦርሳዋን ደግሞ እራሱን በሰንሰለት ከእርሷ ጋር አቆራኝቶ ከኃላዋ ያለው የእሷ እኩያ የሆነ ወጣት ትከሻው ላይ ተንጠልጥሏል።
ከአራት ሰዓት አድካሚ የእግር ጉዞ በኃላ አንድ ሰው አልባ ጎጆ ያለበት ስፍራ ሲደርሱ ርምጃቸው ተገታ።ልጁ ከኪሱ ቁልፍ አወጣና ከእሷ ጋር ሚያገኛኘውን ሰንሰለት በመፍታት ለቀቀው…እሷ እጅ ላይ የታሰረው እንዳለ ስለሆነ ቀሪው መሬት ላይ ይጎተት ጀመር…ከዛ ከመሀከላቸው ሀለቃ መሳዩ ሰው ገፈታተረና ወደጎጆ ውስጥ አስገብቶ ከውጭ ዘጋባት..፡፡ጎጆዋ ዕቃ አልባ ባዶ ነች።በጣም ደክሟትና ሰውነቷ ዝሎ ስለነበረ ወለሉ ላይ ተዘረፈጠችና ግድግዳውን ተደግፋ ትንፋሽ መሳብ ጀመረች።ከላይ የለበሰችው ሹራብ ጨጎጊት በመሰል ነገሮች ተጠቅጥቆበት ተነጫጭቷል፡፡አወለቀችውና በጡት ማስያዣ ብቻ ሆና ሹራብን በተቻላት መጠን ለማፅዳትና ከተጠቀጠቀበት ጨጎጊት ለማስለቀቀ ትጥር ጀመር።ስትጨርስ ባዶ ወለል ላይ መልሳ ጋደም አለች፡፡ብዙም ሳይቆይ ሳታስበው ጭልጥ ያለ እንቅልፍ ወሰዳት፡፡
ኑሀሚ ለምን ያህል ጊዜ እንደተኛች አታውቅም፡፡ስትነሳ ግን አስፈሪ ሁኔታ ላይ ነበረች፡፡ወደ አፍንጫዋ የሞት ሽታ እየተመሰገ ነው፡፡ጉሮሮዋ ላይ መላከ-ሞት የተቀረቀረ መስሎ እየተሰማት ነው...እታች ሆዷ ውስጥ አፉን የከፈተ የመቃብር ጉድጓድ እየታያት ነው።ግን እንደዛም ሆኖ እየፈራች አይደለም። አለመፍራቷ ደግሞ አስደንግጦታል ፡፡ብቸኛ የሚያሳሰባት ነገር የወንድሟ ነገር ነው ፡፡እሷን ማጣቱ በምን ፅናትና ብርታት ይቋቋመዋል?ይሄንን በእርግጠኝነት መመለስ አትችልም፡፡ያው ለእሷ ብቻዋን እንደማትሞት ታውቃለች ፡፡ቢያንስ ቢያንስ ሁለት ሶስት ሰው ይዛ ትወድቃለች፡፡ከሞተች በኃላ ደግሞ የትም ብትሞት የትም ብትቀበር ሀጃዋ አይደለም፡፡እሷ ስኖር ኢትዬጳያዊ ስሞት ኢትዬጵያ ልሁን ከሚሉት መካከል አይደለችም፡፡ለሀገሯ ያላትን ፍቅር እና ለሀገር ያላትን ትርጉም እንጥፍጥፍ አድረገው የተቀበረው ገና ድሮ በልጅነቷ ነው፡፡ቤተሰቦቾ ሲሞቱና ያንን ተከትሎ ቤታቸውም ሆነ ንብረታቸው በብልጣብልጥ ከሀዲዎች ተዘርፎ ጎዳና ተዳዳሪ ሲሆኑ፡፡ሳታስበው ቀስ በቀስ ወደሀገሯ ምድር ወደልጅነቷ በትዝታ ተጓዘች፡፡
ትዝ ይላታል የዛሬ 16  አመት በፊት
ኑሀሚ እና ወንድሟ ናኦል ወላጆቻቸው ሞተው እቤታቸውም ከተወረሰ በኃላ ቀጥታ ሰበታ የሚገኝ ህፃናት ማሳደጊያ ተቋም ነበር የገቡት፡፡እዛ የወላጆቻቸው ናፍቆት ቢኖርባቸውም ያን ያህል የከፋ የሚባል ህይወት አልነበረም ያላቸው፡፡ ግራ መጋባትና ፍራቻ ውስጣቸውን የተቆጣጠረው ጨለማ ስሜት ቢሆንም በአንፃራዊ የተሻለ የተባለ እንክብካቤ እየተደረገላቸውና ትምህርታቸውንም እየተማሩ ከመሰልና እኩያ ወላጅ አልባ ህጻናት ጋር አንድ አመት በተስፋ መኖር ችለው ነበር፡፡በኃላ ግን ነገሮች መስመር የያዙና የሰከኑ በመሰሉ ጊዜ ያልታሰበ ነገር ተከሰተ፡፡አንድ ቀን ኑሀሚ ክፍል ውስጥ ከእኩዬቾ ጋር እየተማረች ሳለች…በህፃናት ማሳደጊያው አስተዳደር ተጠራችና ከክፍል ወጥታ ወደተጠራችበት ቢሮ ሄደች፡፡ቀጥታ ወደዋናው የተቋሙ ዋና አስተዳዳሪ ቢሮ ገባች፡፡ ሽበታሙ አዛውንት አስተዳዳሪ ፊት ለፊት ተቀመጠች ..ኑሀሚ እኚህን ሰውዬ ትፈራቸው ነበር፡፡ ሁልጊዜ ፊታቸው እንደተቋጠረና ሽበት የወረረው አፍሮ ፀጉራቸው እንደተንጨፈረረ ነው፡፡
ድንገት ‹‹ኑኃሚ በቀለ፡፡››ሲሉ ጠሯት

ጭል ጭል በምትል ድምፅ ‹‹አቤት ጋሼ…››አለቻቸው፡፡

ፊት ለፊታቸው ያለውን የዴስክቶፕ ኮምፒተር እስኪሪን እያስተካክሉ…‹‹በዛ ዞረሽ ወደእኔ ነይ፡፡››ነበር ያሏት፡፡
በወቅቱ በጣም ነበር ግራ የገባት…፡፡እኚ ሰው ከሩቅ የሚገፋተር እንጂ እንደዛ በፍቅር የሚያቀርብ ፍላጎት አሳይተዋት አያውቁም፡፡ቢሆንም ትዕዛዛቸውን የማክበር ግዴታ እንዳለባት ታውቃለች፡፡ሁል ጊዜ እሳቸውን ላለማበሳጨትና ላለማስቆጣት እንደጣረች ነበር፡፡በእሷ ግንዛቤ እሳቸው የህፃናት ማሳደጊያ ማዕከሉ ባለቤት ነው የሚመስሏት፡፡በዛም የተነሳ እሷቸውን ድንገት አስቀይማ እሷንና ወንድሟን ከዚያ ብዙ ልጆች ካሉበት ቤታቸው እንዳያባርሯቸው ትሰጋ ነበር፡፡ፈራ ተባ እያለች እንዳሏት አደረገች፡፡ ግዙፉን ጠረጴዛ ዞራ ስራቸው ቀረበች፡፡ ወደራሳቸው ጎተተዋት የተዝረከረከ አለባበሷን አስተካከሉ፡፡የጫረተ ፀጉሯን ወደኃላ እያስተኙ ለማስተካከል ሞከሩ፡፡:እንደዚያ የሚያደርግላት አባቷ

ከመጽሐፍት መንደር💠

06 Oct, 12:05


ኢትዬጵያዊቷ ሰላይ
( በአመዞን ደን ውስጥ)
ምዕራፍ-አራት
ደራሲ-ዘሪሁን ገመቹ ዋቤ
///
ፔሩ/ኢኩኤቶስ
ኑሀሚ በተኛችበት አጨንቁራ በመስታወቱ አሻግራ እያየችው ነው፡፡የህይወት አዙሪት ከየት ወስዶ የት ላይ እንደወረወራት አሰበችና እጅግ ተገረመች፡፡ስለእሱ እና ስለገጠመኞቾ እያመላለሰች በማሰብ ላይ ሳለች ድንገት ወደሀገር ቤት የሚያበር የሀሳብ ሀዲድ በአእምሮዋ ተዘረጋ….ጭንቅሏቷን ትራሷ ላይ አመቻቸችና በተዝናኖት ተኝታ በተዘረጋው ሀዲድ ወደሀገር ቤት በትዝታ ፍስስ አለች፡፡ ኑሀሚ የተደላደለ እና የተረጋጋ የሚባል ህይወት የኖረችው እስከ 9 ዓመቷ ድረስ ብቻ ነበር፡፡ ከዛ በጥምቀት ሰሞን በእለተ ከተራ የዘጠኝ አመቷን የልደት በአል ሊከበርላት ድግስ ተደግሶ፤ ኬክ ታዞ፤ ሻማ ተገዝቶና ፤እቤቱ በዲኮሬሽን አሸብርቆ ባለበት ቀን እናትና አባቷ ተቃቅፈው በተኙበት ሞተው ተገኙ፡፡በምትወዳት የልደት ቀኗ በጥምቀት ቀን ጥር 11 በህይወቷ በጣም ልብ ሰባሪው ሀዘን ደረሰባት፡፡ከዛ በኃላ ህይወት ለእሷ ቀላል ሆና አታውቅም፡፡ከዛ በኃላ በአለም ላይ በ10 ደቂቃ ታላቋ ከሆነ ከመንትያ ወንድሟ በስተቀር ምንም ነገር አልነበራትም….ከዛ በኋላ አመት በመጣ ቁጥር በጥምቀት ወቅት ህዝበ- ክርስቲያኑ በየጎዳናው ተቦት ተከትለው ሲዘምሩና ሲጨፍሩ የወላጆቾን ሬሳ ተከትለው ሙሾ የሚያወርዱ ለቀስተኞች ነው የሚመስሏት…በቃ ከዛ በኃላ ሕይወት በአጠቃላይ ሁሉ ነገር አስከፊ ሁሉ ነገር አስጠዩ ነበር የሆነባት፡፡ይህ በጥልቅ ሀዘንና ብቸኝነት አጥንት የሚሰነጣጥቅ ችግር ለእሷ ብቻ ሳይሆን ለወንድሟም ጭምር ነበር፡፡ስለወንድሟ ትዝ ሲላት ከተጋደመችበት ተስፈንጥራ ተነሳችና ስልኳን በማንሳት ወደ ሀገር ቤት ደወለች…ወንድሟ ጋር፡፡
‹‹ሄሎ ናኦል…እንዴት ነህ?››

‹‹አለሁልሽ እህቴ…እንዴት ነሽ…?.ሁሉ ነገር አሪፍ ነው?፡፡››

‹‹ሰላም ነኝ.. ዛሬ ከፔሩ አንተ ወደምትወዳት ብራዚል እየበረርኩ ነበር… ግን የአየር ፀባዩ ተበላሸና ሳንደርስ አንድ የምታምር ለብራዚል ድንበር ቅርብ የሆነች የፔሩ ከተማ ለማረፍ ተገደድን፡፡››
ወንድሟ በሰማው ዜና በጣም ደነገጠ‹‹እንዴት ….?ምን አይነት ቦታ ነው ያረፋችሁት ..?ፕሌኑ ሰላም ነው?››

‹‹አረ ሁሉ ነገር አሪፍ ነው…፡፡››

‹‹እና እንዴት ልትሆኑ ነው?››

‹‹በቃ ምን እንሆናለን..አሁን ቤርጎ ይዤ አረፍ ብዬ ነው እየደወልኩልህ ያለሁት፡፡ነገ የአየር ፀባዩ ከተሻሻለ እንቀጥላለን፡፡ከለበለዚያ የዝግጅቱ አስተባባሪዎች በሚሰጡት ትዕዛዝ መሰረት የምናደርገውን እናያለን፡፡››
‹‹አህቴ እራስሽን ጠብቂ ደግሞ በጣም ናፍቀሺኛል….ጨርሰሽ እስክትመጪ ቸኩያለሁ፡፡..ሶስት ወር እንደዚህ ረጂም መሆኑን አላውቅም ነበር››ሲል ተናዘዘላት፡፡
‹‹ለምን ይዋሻል..ከዚህ በፊት እኮ ሶስት አመት ሙሉ ተለያይተን ነበር››

‹‹የዛን ጊዜ እኮ እኔ ራሴ ሀይለኛ ወከባ ላይ ነበርኩ…የአዲስአበባ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት አለ..በዛ ላይ በምታውቂው ስራ ሀለቃችን ምስራቅ ከወዲህ ወዲያ ታሽከረክረኝ ነበር…ከዚህ ሁሉ መዋከብ በተረፈቺኝ ብጣቂ ጊዜ ብቻ ነበር አንቺን መናፈቅ የምችለው፡፡አሁን ግን ስለአንቺ ከማሰብ ውጭ ሌላ ምን ስራ አለኝ?››ሲል ተናዘዘላት፡፡
‹‹ስለናፈቅኩህ ደሰስ ብሎኛ፤ቻለው ከአንድ ወር በታች ነው የቀረኝ…እና ደግሞ እንዲህ ዞር ስል የምናፍቅህ ከሆነ ስርህ እያለው አታበሳጨኝም ማለት ነው፡፡››
‹‹አረ አንቺ ብቻ ነይልኝ እንጂ ቀና ብዬም አላይሽም፡፡››ሲል ቃል ገባላት፡፡

‹‹ነግሬሀለው… አሁን የተናገርከውን ሪከርድ አድርጌዋለው፡፡››

‹‹ችግር የለውም እውነቴ ነው፡፡››

‹‹ምስራቅ ደህና ነች..?››ስትል ሌላ ጥያቄ ጠየቀችው፡፡

‹‹ያው ታውቂያለሽ ..እሷ ካልፈለገች አላገኛትም..ግን ደህና መሆኗን አውቃለሁ፡፡››ሲል እሷ ብቻ ሳትሆን ምስራቅም እንደናፈቀችው በሚያሳብቅ የድምፅ ቅላፄ መለሰላት፡፡ምስራቅ ማለት በሁለቱም ህይወት ውስጥ ከፍተኛ ድርሻ ያላት…የደህንነት መስራቤት ውስጥ የምትሰራ ሲኒዬር ሰላይና ለአመታት ሀለቃቸው የነበረች የ43 ዓመት ሴት ነች፡፡
‹‹በል ቸው ..ልተኛ ደክሞኛል ነገ ደውልልሀለው፡፡››አለችው፡፡
‹‹ቸው እህቴ …ውድድ ነው የማደርግሽ››ስልኩ ተዘጋ፡፡
አልጋውን ለቃ ወረደችና ወደ ፍሪጁ በመሄድ ሌላ የቆርቆሮ መጠጥ አወጣችና ከፍታ እየተጎነጨች ወደውጭ ወጣች፡፡ዳግላስ አሁንም ላፕቶፑ ላይ አቀርቅሮ ውዝግብ ውስጥ እንደገባ ነው፡፡የአማዞን ወንዝ ከበረንዳው አሻግረው ሲያያዩ  እንደእባብ ተጠምዝዞ ሽብልል እያለ ሲፈስ ይታያል፡፡ትኩረቷን ወደዳግላስ መለሰችና‹‹እሺ አዲስ ነገር አለ?››ስትል ጠየቀችው፡፡
‹‹የተወሰነ ነገር እየገባኝ ነው፡፡ሳይንቲስት ነኝ፡፡አዎ ኬሚስት ነኝ፡፡እዚህ አማዞን ጫካ ውስጥ በሚገኝ የኮኬይ መቀመሚያ ላብ ውስጥ እሰራ ነበር፡፡አሁንም እንዴት እንደሚቀመም ፕሮሰሱን ሁሉም ትዝ ብሎኛል፡፡ግን ከዛ በፊት የት ነበርኩ..?የት ነው የተማርኩት? ቤተሰቦቼ የት ናቸው…?ሚስትና ልጆች አሉኝ…?እንዴት እዚህ ነገር ውስጥ ልገባ ቻልኩ?አሁንስ ፔሩ ምን ስሰራ ነበር..?የተሸከምኩትን ሻንጣ ሙሉ ዶላር ከየት አመጣሁት? ለምንስ ተሸከምኩት?አሁንስ ወደብራዚል ለምንድነው እየሄድኩ ያለሁት?ቀደም ብለሽ አንቺ ለጠይቅሺኝ ለእነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ሚሆን መልስ ግን እስከአሁን አላገኘሁም፡፡››
‹‹በቃ ላፕቶፑን ዝጋና ተነስ… ወደ ውስጥ እንግባ …ምን አልባት ለጠየቅካቸው ጥያቄዎች ሁሉ የሚሆኑ መልሶችን አረፍ ብለህ እንቅልፍ ከተኛህ በኃላ ትዝ ሊሉህ ይችላሉ፡፡ዶላሩ ላልከው ግን ምን አልባት ለአመታት ለሰራህላቸው ስራ የከፈሉህ ደሞዝ ሊሆን ይችላል፡፡ምን አልባት ከእነሱ ጋር በሰላም ተለያይተህ ሰላማዊና ኖርማል ህይወት ለመኖር ወደ ሀገርህና ቤተሰቦች በመጓዝ ላይ ትሆናለህ፡፡በል አሁን እኩለ ለሊት ሆነ ፤አረፍ እንበልና ነገ ከነገወዲያ የሚሆነውን እናያለን..ምን አልባትም እኮ ለእነዚህ ሁሉ ጥቄዎችህ መልስ የሚሰጥህ ሰው አየር ማረፊያ ቆሞ እየጠበቀህ ሊሆንም ይችላል፡፡››
‹‹አዎ እኔም ተስፋ ማደርገው እንደዛ ነው፡፡››አለና እንዳለችው ላፕቶፑን በመዝጋት መቀመጫውን ለቆ ተነሳ፡፡ ..ተያይዘው ወደ ውስጥ ገቡን ወደበረንዳ የሚያስወጣውን በራፍ በመዝጋት በየአልጋቸው ላይ ተቀመጡ፡፡
‹‹ታውቂያለሽ ከሌላ ፕላኔት ድንገት ተንሸራትቼ የወደቅኩና ያለቦታዬ ከማላውቃቸውና ከማይመስሉኝ ፍጡሮች ጋር የተቀላቀልኩ እየመሰለኝ ነው፡፡››አላት
በንግግሩ አሳዘናት‹‹አይዞኝ…..እንዳልኩህ አሁን መጨነቁን አቁምና ለማረፍ ሞክር…ጥዋት የሚሆነውን እናደርጋለን፡፡›› ብላ አልጋዋ ላይ ወጣችና ተሸፋፍና ለመተኛት መከረች፡፡ፈፅሞ እንቅልፍ ይወስደኛል ብላ አላሰበችም ነበር፡፡ግን ወዲያው ነበር ጭልጥ ያለ እንቅልፍ የወሰዳት፡፡ማለዳ 12፡40 አካባቢ ከእንቅልፏ ባና አይኗን ስትገልጥ ዳግላስ ስትተኛ ተቀምጦበት በነበረበት ቦታ ተቀምጦ ነው ያገኘችው፡፡
‹‹ምነው አልተኛህም እንዴ?››ስትል በመገረም ጠየቀችው፡፡
‹‹አይ አልተኛሁም፡››

‹‹እና እዛው የተቀመጥክበት ቦታ አነጋኸው …. ?››

ከመጽሐፍት መንደር💠

06 Oct, 00:20


ትክክል ነው እስቲ ሴቶች አላችሁ ሃሳባችሁን ሼር አድርጉልን???🙄🙄🙄