የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch @yetewahedoarbegnoch Channel on Telegram

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

@yetewahedoarbegnoch


#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን
ክንድህን ኃይልህንም ጽድቅህንም እስክነግር ድረስ አቤቱ አትተወኝ
#መዝሙር_ዳዊት 70 ( 71 ) 15 – 18
++++++++++++++++++++++
"የመለከቱን ድምፅ የሚሰማ ሰዉ ባይጠነቀቅ፥ ሰይፍ መጥቶ ቢወስደዉ፥ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል።

"የመለከቱን ድምፅ ሰምቶ ስላልተጠነቀቀ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል፤ ቢጠነቀቅስ ኖሮ ነፍሱን ባዳነ ነበር።"
#ትንቢተ_ህዝቅኤል 33፡4-5

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch (Amharic)

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch በአማርኛ ማለት እና ምንም እናምማውን እና አጣምጣምን አቀናብሮ ይገልጹ። ይበልጹ። ስለመቀለብ ዘመንና ዘመን የሚራራውን መዝሙር እየተገለጸው እና እናትዋን ሃይልዋን ጽድቅዋን ባተወኝበት እባክዎ አቤቱን እማ እቸኛዎት ሆነን ማወክ እባክዋን መለከቶችዎን አስተያየልን። በስልጠና የወስበዉን እስከሃይማኖትንና ስትልበት ብሎ ሰይፍዋን ለምንደግፉት እንጂ ቀላልህን ባጭንበት ሦስቸን ሩን ማቀላቀል፣ ቢመጥትስ ቀላልትስ በሁሉም ዕወትናበቴ ለምን። ደሙን አትበል። በማለትም ሰው እንዲድረስ ሰው በደም እንዲሃውል። አስተዳደርም መጠን የሚለው ሰው፣ ያንን የመለከትህን ትንሳኤላችንን መጠን የሚሰማ ሰዉ ጥቅሽ ተወኝ። የመዝሙር ዳዊት 70 ( 71 ) 15-18 እና #ትንቢተ_ህዝቅኤል 33፡4-5 መዝሙር በተገኘው መለከት ሲመልሱ።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

13 Feb, 13:39


በኢትዮጵያ ትንሣኤ ለምታመኑ!!!

...ምድርም ልትፈወስ ፣ እውነተኞች የእግዚአብሔር ሕዝቦች ‹፣ በዚህ ጨለማ በነገሰበት ታላቅ የመከራ ዘመን ፀንተው የተገኙ የሚፅናኑባት ልትሆን ነው ፡፡ ያለፉት አባት እናቶቻችን በገነት ሆነው በልኡል ቅን ፍርድ ሊደሰቱ ነው ፡፡ በመንፈስ አንድነት በልጆቻቸው ሊከብሩ ነው ፡፡

አንዲቷ እምነት የተወደደችው የፀናችው የተቀጠቀጠቸው እምነት የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ፀናች አሸነፈች ፣ ተተከለች ፡፡ እውነተኛ ልጆቿን ይዛ በምድር ላይ ሁሉ ትነግሥ ዘንድ ለቅሬት የታሰቡትን የትንሳኤው ተሸጋሪዎችን አቅፋ ደግፋ በብርሃናዊ አገልግሎቷ ምድርን ልትከድን እነሆ ታሰበች ፡፡

ስማ ! እየሰማህ ሂድ ! ልብ ብለህ አድምጥ አባትህ ዲያብሎስ የቀደመው እባብ ዘንዶው ሃሰተኛው ነብይ ምድርን ከከደናችሁት ከእናንተ ወዳጆቹ ጋር ወደ ሲኦላችሁ ሂዱ ፡፡
እሱም ወደ እስራቱ አንተም ለመጨረሻው ፍርድ ወደ ምትጠበቅበት ሲኦል ልትሰናበት ተወሰነ ስማኝ ! አድምጥ የዲያብሎስ ተጠዋሪ ሁሉ ደህና ሰንብት !!

ከመፅናናት በኋላ በመጨረሻው የፍርድ አደባባይ አንተም ከሲኦልህ እኛም የተሰጠንን የመፅናናት ጊዜ ጨርሰን ከገነት ከአባቶቻችን ጋር ከአባታችን ከመድሃኒያለም እንዲሁም ከእናታችን ከድንግል ጋር ከምንወዳቸው በዘመናችን ሁሉ ሲራዱን ከኖርት ቅዱሳን ሊቀ መላእክት ጋር በእግዚአብሔር የፍርድ ወንበር ከቀኝ በኩል ቆመን ታየናለህ ! ስማ እየሄድክም ቢሆን ለመጨረሻ ልንገርህ ! ምን ይደረግ አንተንም ከጌታ የፍርድ ዙፋን /ወንበር/ ከግራ ቆመህ ለእሳት ልትጣል ልትሰናበት ስትል እናይሃለን ከዘለአለም እስከዘለአለም ከዚያ ወዲያ አንተያይም ፡፡ አንተም ወደታላቁ የገሃነም እሳት ለዘለአለም ስቃይ መሄድ ግድ ነው ፡፡

እኛ ደግሞ የሚወደን አባታችን የናፈቅነው የአብርሃሙ ሥላሴ ወደአዘጋጀልን መንግሥተ ሰማይ በፈንጠዝያ እንገባለን ፡፡ ከዘለአለም እስከዘለአለም እንደ ክዋክብት እናበራለን ፡፡ ለዘለአለም ክብሩን እያወደስን እያመሰገንን እንደመላእክት እንሆናል ፡፡ መቼም ኣታምንምና አታዳምጥም ልብህ በጥርጥር ተሞልቶአልና ይህንን ስንነግርህ እንደምታፌዝ ለሌላ ጥፋት እንደምትዘጋጅ እርግጥ ነው ፡፡ ግን ስማ ! አብቅተሃል ! ተደምድመሃል ! አዋጁም የመጣው አንተንና አባትህ ዲያብሎስን ሊደመድም ነው ፡፡


ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት መልእክት 9 (በድምፅ ክፍል 5) ያለው በቀጥታ የተወሰደ!
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን #ንጉሠ_ነገሥት_ቴዎድሮስ #ቴ #ቶ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

13 Feb, 13:39


በኢትዮጵያ ትንሣኤ ለምታመኑ!!!

👇👇👇🌿

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

12 Feb, 08:41


በቅዱስ መጽሐፍ ስለ ቅድስናዋ እግዚአብሔር ደጋግሞ የመሰከረላት አገራችን ኢትዮጵያ ቅድስት ክብርት አገር ናት፡፡ ሰይጣን በእባብ አድሮ አዳምንና ሔዋንን እንደተዋጋቸው ሁሉ በልዩ ልዩ ሥጋውያንና መንፈሳውያን የውጭ ጠላቶች አድሮ ኢትዮጵያን ሲዋጋ ኖሯል፡፡ዛሬም በመዋጋት ላይ ነው፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትጥቋን አጥብቃ ከቆመች ሳታርፍ፡ ከዘረጋች ሳታጥፍ በኖረችበት ዘመን ሁሉ ኢትዮጵያ ሳትደፈር ኖራለች፡፡ በ፲ኛው ዓመት የጉዲት ወረራ ፡ በ፲፮ኛው መቶ ዓመት የግራኝ ወረራ ፡ በ፲፯ኛው፡ በ፲፰ኛው፡በ፲፱ኛውና በ፳ኛው መቶ ዓመት ተደጋግሞ የደረሰው የካቶሊክ፡ የፕሮቴስታንት፡ የቱርክና የግብፅ ኢስላማዊ ወረራ ተደጋግሞ የከሸፈው ባልተበረዘውና ባልተከለሰው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የእምነት ኃይል ነው፡፡ የአምስት ዓመቱ የፋሺስት ወረራም ጉዳት ማድረሱ የታወቀ ቢሆንም ከሥሩ የተነቀለው ፡ ቁጥቋጦው የተመለመለው እንደ አንበጣ በዝቶ የመጣው የፋሺስት ሠራዊትም የውሃ ሽታ ሆኖ የቀረው በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የእምነት ኃይልና በልጇቿ ደም ነው፡፡
ዛሬ ሁሉ ባላገር ነኝ በማለት ለአገሪቱ ባለ ውለታ መስሎ ይታይ እንጂ ለ ፫ ሺ ዓመታት ለኢትዮጵያ ቆማ የኖረች የሰላም ፋና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ብቻ ናት፡፡
ሊቀ ሊቃውንት አያሌው ታምሩ፡፡

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

07 Feb, 22:23


🟩 🟨 🟥 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን 🟩 🟨 🟥

🗂 #_የኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን መልእክቶች፦

የሚፈልጉትን ጽሑፉ ላይ አንዴ ሲነኩ ወደመልእክቱ ያመራዎታልና፥ አውርደው ያዳምጡ!

⚡️, መልእክት 1 ተጻፈ ኅዳር 7/1998ዓ.ም

⚡️, መልእክት 2 ተጻፈ ግንቦት 27/2000ዓ.ም

⚡️, መልእክት 3 ተጻፈ መጋቢት 19/2001ዓ.ም

⚡️, መልእክት 4 ተጻፈ የካቲት 1/2002ዓ.ም

⚡️, መልእክት 5 ተጻፈ መስከረም 21/2004ዓ.ም

⚡️, መልእክት 6 ተጻፈ ታኅሣሥ 19/2007ዓ.ም

⚡️, መልእክት 8 ተጻፈ ታኅሣሥ 21/2011ዓ.ም

⚡️, መልእክት 9 ተጻፈ ታኅሣሥ 21/2013ዓ.ም
        ➥ቁጥር 9_ክፍል 1
        ➥ቁጥር 9_ክፍል 2
        ➥ቁጥር 9_ክፍል 3
        ➥ቁጥር 9_ክፍል 4
        ➥ቁጥር 9_ክፍል 5

መልእክት 10 (ክፍል 1-7) ተጻፈ ጥር 7/2015 ዓ.ም
°°°°° °°°°° °°°°° °°°°° °°°°°
⚡️, ከመልእክት 1—6 & 8 በጽሑፍ (PDF)

⚡️, መልእክት 9 በጽሑፍ (PDF)

, መልእክት 10 በጽሑፍ (PDF)

⚡️, ደብዳቤዎች በድምፅ
⚡️, ደብዳቤዎች በጽሑፍ(PDF)

⚡️, ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በየጊዜው የተሰጠና የተላለፈ ምክር፣ ማሳሰቢያ፣ መመሪያ፣ መግለጫ፣ ትዕዛዝ፣ ትምህርቶች ወዘተ በቅደም ተከተል

°°°°° °°°°° °°°°° °°°°° °°°°°
☑️ መልእክታቱን በተለያየ ቋንቋ በአንድ ስፍራ ለማግኘት t.me/ethioBirhan መከታተል የሚችሉ ሲሆን ለዚህ ቻናል የተሠራውን ማውጫ ደግሞ t.me/EthioLightContents ላይ ማግኘት ይቻላል!

🌿 እንዲሁም ሁሉንም ኢ/ዓ/ብ መልዕክታት ፤ ትምህርቶችና መግለጫዎች... ብቻ በአማርኛ ቋንቋ የቀረቡትን በቅደም ተከተል ከተለቀቁበት ጊዜ ጋር በቀላሉ ለማግኘት t.me/Amharic_Messages ላይ መከታተል ይችላሉ።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

02 Feb, 14:45


ቅዱስ መርቆሪዎስ
...በመጨረሻም ህዳር ፳፭ ቀን አንገቱን ቆርጠው ገደሉት ደም ውኃና ወተት ከአንገቱ ፈሰሰ። መርቆሬዎስ ከዕረፍቱም በኋላ ብዙ ተአምራትን አድርጓል፤ ፈረሱ ለሰባት ዓመት ወንጌልን አስተምሯል፤ በኋላም አንገቱን ቆርጠው ገድለውታል እንዴት ብሎ የሚገረም የበልአምን አህያ ይጠይቃት፤ እኛስ እስመ አልቦ ነገር ዘይሳኣኖ ለእግዚያብሔር ብለን እንመልሳለን:: ዘኁልቁ 22፡28

የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕልም በአዎንታ አንገቱን ዘንበል አድርጎ ምስክርነት ሰጥቷል። ይህም ሊታወቅ ዛሬ በሀገራችን በምድረ ተጉለት በስሙ ከታነጸ ቤተ ክርስቲያን ካህናት ደነነ ስዕሉ እያሉ ሲዘምሩ ጎንበስ ቀና ሲሉ እንደሚታይ ይነገራል። የሰማዕቱ የቅዱስ መርቆሬዎስ ረድኤቱ በረከቱ አማላጅነቱ ቃል ኪዳኑ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

24 Jan, 13:02


ወገኖቼ ኢትዮጵያውያን ! አገራችን መጠለያችን እንድትጠፋ እሷንም የሚወዱ ልጆቿ ከእምነታቸው እንዲከስሙ ተወስኖ መስራት ከተጀመረ ብዙ ዘመናትና አመታት አልፈዋል፡፡ አንድ ህዝብ፣ አንድ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት፣ አንዲት አገር፣ አንዲት አረንጉአዴ ቢጫ ቀይ ባንዲራ ብሎ ያመነና በዚህ የጸና ወገኔ ወንጀለኛ ነው፤ ስለሆነም ይሳደዳል ይገደላል ይታሰራል ቢዘረዝሩት ብዙ ነው፡፡ያለቀውና የደቀቀው ማንነትህ ይገልጸዋልና !! ትግስቱ የማያልቅበት አምላክ አሁን ግን ትእግስቱ አለቀና አበቃ ! በስጋችንም ያመንናቸው ያደራጀናቸው ተበተኑ፡፡ ተስፋችን ጨለመ፤ በመሆኑም መታመኛ ጥበብ ሁሉ አለቀ፤ በመሆኑም ይህን የተመለከተው አምላካችን ትግስቱ ተሟጧል ! የማዳን ክንዱን አነሳ፤ ፍርዱን እንደጸሀይ ሊያወጣ ከሰማይ ማንጎዳጎድ ጀመረ !! ተስፋህን አለምልም ወገኔ አባትህ የታመነው ጌታ ደርሱአል !!!

''አንተ ባህርን በክንድህ አጸናሃት፤ አንተ የእባቦችን ራስ በውሃ ውስጥ ቀጠቀጥህ ( ሰበርህ ) አንተ የዘንዶውን ራሶች ቀጠቀጥህ ለኢትዮጵያ ህዝቦችም ምግብን ሰጠሃቸው!''
መዝሙረ ደዊት 73 ( 74 ) 13 – 14
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን #ቶ #ቴ #ንጉሠ_ነገሥት_ቴዎድሮስ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

22 Jan, 07:40


'' ብርሃንም በጨለማ ይበራል፥ ጨለማም አላሸነፈውም።''
የዮሐንስ ወንጌል 1 : 5

ስለ ሁሉም ነገር ልዑል እግዚአብሔር ይመስገን!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

20 Jan, 08:13


"ከዱር ፡ እያገሳ ፡ ሲወጣ ፡ ያንም ፡ ንሥር ፡ በሰማኸው ፡ ነገር ፡ ሁሉ ፡ ሲናገረውና ፡ በኃጢአቱ ፡ ሁሉ ፡ ሲዘልፈው ፡ ያየኸው ፡ ይህ ፡ አንበሳም ፡ ልዑል ፡ በኋላ ፡ ዘመን ፡ የጠበቀው ፡ ከዳዊት ፡ ወገን ፡ የሚወለደው ፡ ነው፡፡ መጥቶም ፡ ኃጢያታቸውን ፡ ይነግራቸዋል ፡ ስለበደላቸውም ፡ ይዘልፋቸዋል ፡ በፊታቸውም ፡ ፍዳቸውን ፡ ይገልጥባቸዋል ። በሕይዎት ፡ ላሉም ፡ አስቀድሞ ፡ በፍርድ ፡ ያቆማቸዋል ፡ ከዘለፋቸውም ፡ በኋላ ፡ ያን ፡ ጊዜ ፡ ያጠፋቸዋል።"

(እዝራ ሱቱኤል 11፥ 31-32)

🔴 ንሦሩ በዲያቢሎስ የሚመራው የዚህ አለም የጨለማ ስርአት ነው፣ አንበሳውም አሁን በዚህ ዘመን የሚገለጠው የሥላሴ ባሪያ የድንግል ባሪያ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ነው። እግዚአብሔር በሱ ላይ አድሮ በኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት አማካኝነት ኃጢአታቸውን ይነግራቸዋል፣ ስለ በደላቸው ይዘልፋቸዋል፣ በፊታቸውም ፍዳቸውን ይገልጥባቸዋል፣ በህይወት በፍርድ ይቆማቸዋል ፣ ከዘለፋቸውም በኋላ ያጠፋቸዋል ። የዚህን ዓለም የጨለማ ሥርአት የሚያጠፋው በኢትዮጵያ የሚፀናው ብርሃናዊው መንግሥት ነው።

ብቻ አንደበትም ቃላትም የለኝም እምየ ማርያም ከአንደየ ልጇ ጋር ትክበር ትመስገን። አሜን!!!

ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር!
ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም!
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን!
ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዥ!
🙏🙏🙏

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

19 Jan, 08:02


በወንዶ ወረዳ የሰደድ እሳት ተከስቷል

አዲስ አበባ፣ ጥር 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በወንዶ ወረዳ ዛሬ ከቀኑ 10:00 ላይ የሰደድ እሳት አደጋ መከሰቱ ተነግሯል።

በወረዳዉ ጎቱ ኦሎማ ቀበሌ በተለምዶ አባሮ የሚባል ተራራ ደን ላይ እሳት መቀጣጠሉ ነው የተገለጸው።

በዚህ ምሽትም እሳቱን ለማጥፋት ርብርብ እየተደረገ ሲሆን፥ ፋና ዲጅታል የአደጋውን ምንጭ መጠንና ስፋት እንዲሁም ሰደድ እሳቱን በቁጥጥር ስር ለማዋል የሚደረገውን ጥረት አጣርቶ በዝርዝር ያቀርባል።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

18 Jan, 09:01


ጾመ ገሃድ (ጋድ) የቃሉ ትርጉም "ገሃድ" ሲል መገለጥ "ጋድ"ሲል ለውጥ ማለት ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደቱና የጥምቀቱ በዓል በሳምንት ሁለት ቀን በምንጾምባቸው ጾም በተሠራባቸው በረቡዕና በዓርብ የዋለ እንደሆነ የጾሙ ሥርዓት ሳያጠበቅ ፡
፩ኛ፡ ታህሣሥ ፳፰ ቀን ለ ፳፱ አጥቢያ፡
፪ኛ፡ ጥር ፲ ቀን ለ ፲፩ አጥቢያ በመንፈቀ ሌሊት ቅዳሴ እንዲፈፀምና ምእመናን በትንሣኤው የአከባበር ሥርዓት ዓይነት በዓሉን በደስታ እንዲያከብሩ አዝዘዋል፡፡ ስለዚህ የሁለቱም ማለት የልደት የጥምቀት ዋዜማ በጾም እንዲታሰብ ሆኗል፡፡ በአንድ በኩል የጌታን መገለጥ የምናስብበት ነው፡፡
መገለጥ ሲባልም እንደ በዓላቱ ጠባይ ሁለት ነው፡፡ በልደት መገለጥ ሲባል ሰው ሆኖ የማያውቅ አምላክ በሥጋ ሰው ሆኖ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ ስለተገለጠና ሰዎች ሊያዩት ሊዳስሱት ስለቻሉ ነው፡፡
በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ ፴ ዓመት ዕድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲሕ የሆነው አምላክ አማኑኤል ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በሁዋላ በ ፴ ዓመት ዕድሜው በዮርዳኖስ ወንዝ በዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ፡ "የምወደው ልጄ ይህ ነው እሱን ስሙት" ብሎ በሰጠው ምስክርነት ፡ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት የተነበዩለት የሰው ልጆቾ መድኃኒት ሥግው አምላክ ማለት ሰው የሆነ አምላክ እሱ መሆኑ ስለተገለጠበት ነው፡፡
ጾመ ገሃድ ወይም ጋድ ቅዳሜ፡ እሁድ ቢሆን በሰንበት ጾም ስለሌለ ሥርዓተ ጾሙ ከጥሉላት ምግብ በመከልከል ብቻ ይፈፀማል፡፡
አለቃ አያሌው ታምሩ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

18 Jan, 09:01


በዕንተ ጾመ ገሃድ (ጋድ) - ጥር 10

- በዚች ዕለት ምንም ምን መብልን ሰይቀምሱ ምእመናን ሁሉ እስከ ምሽት ይጾሙ ዘንድ ከእኛ አስቀድመው የነበሩ ታላላቅ ሊቃውንት የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓትን ሠሩ በምሽትም ቢሆን በታላቁ ጾም ከሚበላው በቀር ጥሉላትን እንዳይቀምሱ። በዚች ዕለት ምእመናን እስከ ምሽት እንደመጾሙን ያዘዙበት ምክንያቱ ይህ ነው የልደትና የጥምቀት በዓል በዓል በረቡዕ ወይም በዓርብ ቀን ቢሆን በበዓለ ኃምሳ የሚበላውን የጥሉላት መብል በጥዋት በመብላት ምእመናን ሁሉ በዓሉን እንዲአከብሩ የከበሩ አባቶቻችን ሐዋርያት አዝዘዋል እሊህ ሁለቱ የእግዚአብሔር ታላላቅ በዓላቶቹ ናቸውና።

- እኛ በዚህ በኅላፊው ዓለም ተድላ ደስታ ደስ የሚለን ለሌሎች እንዳይመስላቸው እንደ አይሁድና እንደ አረማውያን በዓል በመብልና በመጠጥ ብቻ እንዳናደርግ ስለዚህ ከልደትና ከጥምቀት በዓል በዋዜማ ያሉትን ሁለቱን ዕለታት እንድንጾም አዘዙን የልደትና የጥምቀት በዓል በረቡዕና በዓርብ ላይ በሚሆን ጊዜ በረቡዕና በዓርብ ፈንታ እንድንጾማቸው ይገባልና በዚህም ሁለት ሥራ ይፈጸምልናል የጾም ሥራና የበዓል ማክበር ሥራ ነው። እንዲሁም በግብፃውያን አብያተ ክርስቲያን የተሠራ ነው።


- በይረሙን በእሑድ ወይም በአይሁድ ሰንበት ቀን ቢሆን ይህም ጌታ የተገለጸበት ጥር ዐሥራ ቀን ነው በዋዜማው ዐርብ እስከ ምሽት ይጹሙ አስቀድመን እንደተናገርን ጥሉላት አይብሉ የልደትና የጥምቀት በዓልም ሰኞ ቀን ቢሆን በሰንበት ቀን ይጾም ዘንድ አይቻልም ነገር ግን ጥሉላትን ከመብላት ይጠበቁ።

- በጥምቀትም ዕለት ከእኵለ ሌሊት በፊት ተነሥተው በውኃው ላይ ይጸልዩና ይጠመቁ ሕፃናትም በሚጠመቁ ጊዜ በውኃ እንዳይገድፉ ካህናቱም ከመንጋቱ በፊት ቀድሰው ቊርባኑን ያሳርጉ እጅግም ማልደው በጥዋት ከቤተ ክርስቲያን ይውጡ በከበረ ሥርዓታቸው ጌቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙ።

- የመለካውያን ወገኖች ግን የልደትና የጥምቀት ዋዜማ በቅዳሜ ቀን ወይም በእሑድ ቀን ቢሆን በሦስት ሰዓት ይቀድሳሉ ከወደዱም የተባረከ ኅብስት ተመግበው ውኃ ይጠጣሉ ከዚህም በኋላ ካህናቱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሁነው በየሰዓቱ በመጸለይ ለበዓሉ የሚገባውን የነቢያትን ትንቢቶች ያነባሉ በዚያች ቀን በምሽት ይኸውም ጥር ዐሥር ነው በውኃው ላይ ይጸልያሉ ይህም አባቶቻችን ሐዋርያት እንዳዘዙት አልሆነም። እርሳቸው የኤጲፋንያን በዓል እንዲአክብሩ አዘዋል ይኸውም መድኃኒታችን የተገለጠበት ካኑን በሚባል በሮም ሁለተኛ ወር በሰባት ይህ ጥር ዐሥራ አንድ ቀን ነው።

- መለካውያን ግን የከበሩ አባቶች የቤተ ክርስቲያን መምህራን ያዘዙትን ይተላለፋሉ በልደትና በጥምቀት በዓል ዓርብም ረብዕም ቢሆን አስቀድመው በርሱ ፈንታ ሳይጾሙ በጥዋት ተነሥተው ይበላሉና። እኛንም ከበደላችን ያነጻን ዘንድ በዮርዳኖስም ወንዝ እንደ ተገለጸ የጌትነቱን ክብር በልቡናችን ይገልጥልን ዘንድ የክብር ባለቤት የሆነ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን እንለምነው ጌትነት ክብር ስግደት ለእርሱ ይገባልና ከቸር አባቱ ጋር ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

18 Jan, 07:45


https://youtu.be/2T2YRoXQ-_Y?si=Nhh4BdaHe7WmkpQa

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

18 Jan, 07:45


ውብነህ(አሞራው) አንድ ቀን ለአደን እንደወጡ ከዋሊ ዳባ ዋልድባ ገዳም ውስጥ ይደርሳሉ። በዚያም አንድ የበቁ ባሕታዊ ያገኟቸዋል።

ውበነህ አስቀድመው ለሀገራቸው የተጠሩ ነበሩና ባሕታዊው ሰው “ምነው ውብነህ ለምን አሁን ትተኩሳለህ ወደፊት ሀገርህን ለመቀማት ከሚመጣው ጠላት አትተኩስም ወይ ?” አሏቸው። ብልሁ አዳኝ ውብነህም እባክዎ አባቴ ባዕትዎትን(የፀሎት ቤት) ያሳዩኝ አሏቸው። ባሕታዊው ሰውም ውብነህን አስከትለው ወደ ባዕታቸው ሄዱ። ወደ ዋሻ ውስጥም አሰገቧቸው። ቀን ቀን ገዳሙን እንዲያገለግሉ ማታ ማታ ደግሞ ከደጅ እንዲተኙ አዘዟቸው። የተባሉትን በቅንነት ፈፀሙ። ሶስት ወራትም ሞላቸው። በዚያም ጊዜ ባሕታዊው ሰው “ልጄ ሆይ የእናትህን ለቅሶ ጌታ አይቷል።
ከነገርኩህ ነጭ ጠላት ኢትዮጵያን ነፃ እንድታወጣ ከእግዚአብሔር ስልጣን ተሰጥቶሃል። ንጉሡንም ከሥደት ትመልሰዋለህ። ዋጋሕን አይከፍልም። ያንተን ዋጋ የሚከፍሉሕ ሥላሴ ናቸው።” ብለው መርቀው አሰናበቷቸው። ውብነህ አደን አቆሙ። አስቀድሞ የተነገራቸው የመከራ ጊዜ ደረሰ። የሚወዷት ሀገራቸውን ጠላት ወረራት።

++++++++++++
በዚያ ዘመን የጠላትን ስንቅና ትጥቅ የያዘ አርባ መኪና ወደ ጎንደር ለማለፍ ዳባት ላይ መድረሱን አሞራው ሰሙ። በጠፍ ጨረቃ ገስግሰው አምባ ጊዮርጊስ ላይ አርበኞችን አስደፍጠው መንገድ ላይ ተጠባበቁ። የጣልያን መኪና ሲደርስ የደፈጣ ተኩስ ከፍተው አርባውን መኪና ማረኩ ይባላል።

በሌላ ጊዜ ደግሞ የጠላት ጦር ጎንደር ተነስቶ በለሳ ደረሰ። የአሞራው ውብነህ ጦር ከሌሎች አርበኞች ጋር አጣጥ መጠበቂያ ከተባለው ተራራ አካባቢ ገጠመው። የፋሽስት ጣልያን ጦር ተደምስሶ የጦር አዛዣቻቸው ከጥቂት ወታደሮች ጋር በመሆን እግሬ አውጭኝ ብሎ ፈረጠጠ፡፡ በዚህም ጊዜ እንዲህ ሲሉ ተቀኙላቸው፡፡

ʺየሰማዉን እንጃ ሮም ገስገሰ፣
የጦሩ መድሃኒት አሞራው ደረሰ።
ያየህም ተናገር የሰማህም አውራ፣
ተገናኝቶ ዋለ አሞራው ካሞራ።

ጎንደር ከግንቡ ላይ ያለው ነጭ አንበጣ
ከምን ሊገባ ነው አሞራው ሲመጣ፡፡”

በየደረሱበት ሁሉ ጠላት የሚበረግግላቸው፣ እንደ መንጋ የሚነዳላቸው፣ ዓልሞ የማይስተው ዓይናቸው፣ የማይደፈረው ክንዳቸው፣ ሰው ሆነው ሳለ እንደ አሞራ የሚያደርጋቸው፣ በጠላት አናት ላይ እንደ አሻቸው የሚከንፉት፣ ጀግንነታቸው ሀገሬውን አጀብ አስባለው፡፡

ʺእንኳን ኢትዮጵያ ባለቤትዬው
ጣልያንም ቀና አንድ ቀን ባዬው” እንዳለ አርበኛው የአሞራው ጀግንነት ለወዳጅ ብቻ ሳይሆን ለጠላት ገረመው፡፡ አሞራው
በየደረሱበት ጠላትን ድባቅ እየመቱ የአካባቢውን አስተዳደር እያጠናከሩ አያሌ ጀብዱዎችን ይፈጸሙም ነበር ፡፡
+++++++

“ንጉሡ ተሰደው ያልሆነላቸውን
ራስ ደጅአዝማቹ ያልሆነላቸውን
ይነዳው ያጉዘው ጀመረ አሞራው ብቻውን” እየተባለላቸው የጣልያንን ሠራዊት እንደአሻቸው ይነዱት ነበር።
++++
“የሮም ነጭ በሬ ተከቧል በብረት፣
ሊበላው ነው መሰል አሞራው ዞረበት”

ʺጎንደር ከግንቡ ላይ ያለው ነጭ አንበጣ
ከምን ሊገባ ነው አሞራው ሲመጣ”
ʺበአርማጭሆ መንገድ፣ በወገራ መንገድ፣
በስሜንም መንገድ፣ በመረባም መንገድ፣
በበለሳም መንገድ አይተላለፉ፣
አሞራው አርበኛ ይማታል በክንፉ።
የሮማ ነጭ በሬ ተከቧል በብረት ፣
ሊበላው ነው አሉ አሞራው ዞረበት፡፡”

እኒህ ጀግና ከነጻነት በኋላ በጎንደር አደባባይ ለኢትዮጵያ ጦር ድጋፍ ያደረገው የእንግሊዝ ባንዴራ ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ጋር ሊወለበለብ ሲል አሻፈረኝ ብለው የሀገራቸውን ሠንደቅ ብቻ እንዲውለበለብ ያደረጉ መሆናቸውም ይነገርላቸዋል፡፡ በአንድ ሀገር አንድ ሠንደቅ እንጂ ሁለት አይፈቀድም፣ የሚፈቀደውም አርንጓዴ፣ ቢጫ፣ ቀዩ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ነው ያሉ ሰው ናቸው።
በእሳት ውስጥ ተፈትነው ሀገራቸውን ከጅብ አፍ ያተረፉት ራስ አሞራው መስከረም 6 ቀን 1975 ዓ.ም ነበር ሕይወታቸው
ያለፈው፡፡ በእሳት የተፈተነ ዘመን አልፈው ያልተደፈረች ሀገር፣ ያልተቀናነሰ ክብር፣ ያልደበዘዘ የሀገር ፍቅር፣ በፈተና የማይናወጥ የጀግንነት ሚስጥር አውርሰዋልና ስምዎ ከፍ እንዳለ ይኖራል።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

13 Jan, 12:57


ደስ ይበላችሁ በአለም የሚያበራ ክብር ለኢትዮጵያ ተሰጥቷል!!!

#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

12 Jan, 05:35


https://www.youtube.com/watch?v=R3vzN7Vl7H8

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

11 Jan, 12:09


🔴ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 3 ስለ አሜሪካ (ባቢሎን) እንደዚህ ብሎ ነበር 👇👇👇

...አሜሪካ የምንዝርና ኢንዱስትሪ ምንጭ፣ የሃብት ምንጭ፣ የጥንቆላ ፣ የመተት አፍላቂ፣ አሜሪካ የመንግስታዊ ዘረፋ መሃንዲስ፣ አሜሪካ ጨፍጫፊ፣ አሜሪካ የዘረኞች ምሽግ፣ አሜሪካ የጨለማ ተግባር ሁሉ ማመንጪያ ናት፡፡

አሜሪካ በጥበቧ የተመካች በሳይንስ የቁስ ውጤቷ የታበየች በግልጽና በማያሻማ አቋም የልዑልን ሕግ አፍርሳ፣ ከሌላውም አለም ጠርጋ፣ በየትኛውም የአለም ክልል የዲያቢሎስን ሕግ ተክታ ለተካችውም የጨለማ ሕግ ቆማ እየተዋጋች ያለች ናት፡፡ የፈጣሪን ልጆች ከምድር ገጽ ለማጥፋት የተቃረበችም ናት፡፡ ውጤቱም በግልባጭ መሆኑ ባይቀርም፡፡
ትንቢተ ኢሳኢያስ፡ ም. 47፡ በሙሉ

በሁለቱም መልእክቶች እንደተጠቀሰው እስትንፋስ የለም፡፡ እቅድ ድርድሩ መላ አደራጁ፣ የዲያቢሎስ ልጆች መቼም ቢሆን ምላሳችሁ አይሞትም፡፤ አባታችሁ ዲያቢሎስ ባሳደጋችሁ መንገድ በጨለማው እየተደናበራችሁ ወደ መጨረሻው ሞታችሁ ትዘልቃላችሁ እንጂ መመለስ የለም፡፡
🔴› ከውስጧ የሚወጡ ሰዎች በእሳቱ ሲጤሱና እሳቱ ሲነድ ለአለም ሁሉ ይታያል ለታመኑ ወዳጆቿም ይተርፋል፡፡
🔴› ከውስጡ የሚወጡ ሰዎች ቢኖሩም ለረጅም ጊዜ የፍርሃትና ድንጋጤው ጥላ-አይርቃቸውም፡፡
🔴› ለጥፋት ያሰናዳቸው መሳሪያ ሁሉ የትም ታኑረው የት ወዳጅ ከምትላቸው ጋር አብሮ ይጠፋል፡፡ ምልክቱም አይገኝም፡፡
🔴› የሰው ዘር፣ ለመግዣ፣ እምቢ ቢል፣ ለመጨፍጨፊያ ያዘጋጀችው/ያዘጋጃችሁት/ ኒክለር፣ ኬሚካል፣ ባዮሎጂካል፣ መሳሪያ ጀት፣ መርከብ፣ ሳተላይት መርዝ ሁሉም ከነአዛዦቹ፣ ከነአድራጊዎቹ፣ ከወሳኞቹ ጋር አብሮ ይጠፋል፡፡
🔴› በዚች በባቢሎን አገር የበቀለ ማንኛውም የትሃጢያት ማጎልመሻ ፣ ማራመጃ፣ የዲያቢሎስ መጠቀሚያ በሙሉ ይጠፋሉ፡፡ በውስጡ ያሉ ሶዶማውያን አመንዛሪዎች፣ ነፍሰ ገዳዮች፣ በሃብታቸው፣ በእውቀታቸው የሚጨማለቁ ሁሉ የፈጣሪን ህግ የናቁ ሁሉ የእምነት መሪም ተመሪም ነን የሚሉና እውነትን የናቁ /ካቶሊክ፣ ሙስሊም፣ ፕሮቴስታንት፣ ቡዲሂስት፣ ኮሚኒስት፣ ሌሎችም/ የጦር መሪ ነን፣ የጸጥታ ሃላፊ ነን፣ የምክር ቤት አባል ነን፣ ሴናተር ነን፣ አገረ ገዥ ነን፣ ባለኩባንያ ነን፣ ሊቅ ነን፣ የሚሉ ሁሉ በውስጧ የበቀሉ እሬቶች ሁሉ ይጠረጋሉ ይጠፋሉ፡፡
🔴› ምድሪቱ ከተሸከመቻቸው ሁሉ አውሬዎች ትጸዳለች ትላቀቃለች፡፡
🔴› ባቢሎን ለሰው ዘር የደገሰችው ሁሉ ለራሷ የምትጋተው ይሆናል፡፡ ቁጣው ሲፈስስ ማን ያመልጣል? ማንም አያመልጥም እሳቱ ሳይፈትሸው የሚያመልጥ የለም፡፡ በግንባሩ ምልክት ካለው ይድናል፡፡ ከሌለው የለም፡፡

ምንጭ:- ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 3 (መጋቢት 19/2001 ዓ.ም)

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

11 Jan, 12:09


🔴ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 3 ስለ አሜሪካ (ባቢሎን) እንደዚህ ብሎ ነበር 👇👇👇

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

10 Jan, 08:33


https://youtu.be/Apkml-Vrk98

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

10 Jan, 05:17


❗️በጋሞ ሰማይ ሥር የታየው ያልተለመደ ብርሃን በሰማይ ላይ ነገሩ ተፈጥሯዊ ይሁን ሌላ ሰው ሰራሽ ክስተት እሥከ አሁን ምንም የተባለ ነገር የለም ።

👀ባለፈው ሳምንት በኬኒያ ምድር ወደ 500k.g የሚጠጋ ምንነቱ ያልታወቀ ብረት ከሰማይ መውደቁ ይታወቃል።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

10 Jan, 05:02


ያልተለመደ ክስተት በሰማይ ስር

ይህ ምልክት የታየው በወላይታ፣ ጋሞ፣ ጎፋ፣ ዱራሜ፣ ሀዋሳ፣ ቡሌ ሆራ፣ ኮንሶ፣ ቡርጂና በመሳሰሉት ሰማይ ሥር ለጊዜው ምንነቱ ያልታወቀው በኢሳት እየቀጣጠለ ብርሃን እየፈነጠቀ በሰማይ ላይ እንዳለፈና እያለፈ እንደሆነ የአይን እማኞች አረጋግጠውልኛል።

ነገሩ ተፈጥሯዊ ይሁን ሌላ ሰው ሰራሽ ክስተት አልታወቀም። አንዳንዶች መነሻው ያልታወቀ ሚሳኤል ይላሉ። ሌሎች ደግሞ አይሮፕላን መሳይ ይላሉ።

ይሄው በራሪ አካል ከላይ የተጠቀሱ ሥፍራዎችን አቋርጠው ወደ ጂንካ መስመር እየተጓዝ እና በጉጂ አከባቢም እንደታይ ታውቋል።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

09 Jan, 12:47


https://www.facebook.com/share/v/15pNnQF2WR/

በካሊፎርኒያ የተከሰተው ሰደድ እሣት በፍጥነት እየተዛመተ ነው። በጥቂት ሰዓታት ውስጥ በርካታ ሄክታር መሬት አዳርሷል። ነዋሪዎች ቤት ንብረታቸውን፤ መኪናቸውን ጥለው ሸሽተዋል።
https://bbc.in/4jan4ZF

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

08 Jan, 08:29


አሁን ስንዴውን ወደ ጎተራ እንክርዳዱን ለእሳት!!!

#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

08 Jan, 06:34


🔴" የጎበዝ ያለህ "‼️

ከዚህ ቀደም በሙዳይ መጽሔት " የሰው ያለህ " የሚል ጥሪ ማስተላለፌ ትዝ ይለኛል። አሁን የሰው ያለህ አይደለም የምለው አሁን " የጎበዝ ያለህ " ነዋ ጠንክሮ የሚከላከል ለሃይማኖቱ ፣ ለቤተ ክርስቲያኑ ፣ ለትምህርቱና ለሥርዓቱ በአንድ ኀብረት ፣ በአንድ ልብ ፣ በአንድ አፍ የሚከላከል ያስፈልጋል። ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የኢትዮጵያን ሀብት ናቸው። ሁሉም አትኩሮ ሊጠብቃቸው ይገባል።

ክቡር አለቃ አያሌው ታምሩ
አለቃየ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

07 Jan, 05:41


https://youtu.be/OdUXKEIYpag

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

05 Jan, 12:01


የኢትዮጵያ ትንሳኤ!!!

#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

04 Jan, 13:29


ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን🌍 🔴መልእክት አንድ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

04 Jan, 13:29


ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን🌍 🔴መልእክት አንድ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

03 Jan, 10:36


#አፋር በተደጋጋሚ ሲከሰት የነበረን የመሬት መንቀጥቀጥ ተከትሎ ዛሬ ጧዋት በአፋር በዱለሳ ወረዳ ሰገንቶ ቀበሌ የእሳተ ጎመራ ፍንዳታ ተከስቷል።
=========================
-👆እሳተ ገሞራዎች ፦ የተኙት ነቅተዋል።
ሰው ያላየውንም ጥፋት ያመጣሉ።
አሁንም እያጠፉ ይገኛሉ።
⚡️ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልእክት 5 ገጽ 16
ተጻፈ 21/01/2004 ዓ,ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

02 Jan, 07:13


ታህሳስ 24 - የታላቁ አባት አቡነ ተክለሃይማኖት ልደት
🌿🌿🌿🌿🌿🌿

ታህሳስ 24 በዚህች ቀን ታላቁ ጻድቅ አቡነ ተክላሃይማኖት የተወለደበት ቀን ነው፡፡ የትወልድ ቦታቸው ሽዋ ፀላልሽ አወራጃ በዘረሬ ነው: የአባታቸው ሰም ፀጋ ዘአብ የእናታችው ስም እግዚሐርያ ይባላሉ መካን ነበሩ ልጅ አንዲሰጣቸው ወደ እግዚአብሔር ዘወትር ይፀልዩ ነበር መጋቢት 12 ቀን እንዲህ ሆነ መቶሎሜ የተባለ ጣኦት አምላኪ ንጉስ አገራቸውን ወረር መንደሩንም አጠፋ ፀጋ ዘአብ ወንዝ ዉስጥ ገበቶ አመለጠ እግዚሐርያ ግን ተማርካ ሄደች፡፡ በጣም መልከ መልካም ሰለ ነበረች መቶሎሜ ሊያገባት አሰበ ታላቅ ድግስም ደገሰ አገር ምድሩ ተሰብስቦ ሲዘፍን ሲጨፍር ሳለ ቅዱስ ሚካኤል ታላቅ መብርቅ ነጎድጓድ አሰማ ብዙዎች ሞቱ እግዚሐርያን በክንፎ ተሸክሞ ዞረሬ ከቤተክርስቲያን ዉስጥ አስቀመጣት ከባለቤቷ ፀጋዘአብ ጋር ተገናኙ ተቃቅፈዉ ተላቀሱ ከሁለት ቀን በኋላ መጋቢት 24 ቀን አቡነ ተክለሃይማኖት ተፀነሱ በዛሬዋ ቀን ታህሳስ 14/ 1167 ዓ/ም ተወለዱ ቀኑ አርብ ነበር : በተወለዱ በ3ኛ ቀናቸዉ እሁዱ በ3 ስዓት "አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ አብ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ" ብለዉ ስላሴን አመሰገኑ፡፡

አባታችን የእንድ ዓመት ከመንፈቅ ህፃን እያሉ በድፍን ሽዋ ረሃብ ተከስቶ ነበር በተለይም በዞርሬ እግዚሐርያ አዘነች አለቀሰች እርቧት ነው ጠምቷት ነው ቢሉ የለም እርቧትስ ጠምቷትስ አይደለም የቅዱስ ሚካኤል ዝክሩ ታጎለብኝ ብላ አንጂ፡፡ ህፀኑ ተክልዬ ከእናቱ ጭን ወርዶ እየዳኸ ወደ ጓዳ ሲሄድ እናቱ አቀፈችዉ እርሱ ግን አለቀስ፡፡ ዶቄት የተቀመጠበትን እንቅብ እንድትስጠው በእጁ ጠቆማት ሊጫወትበት መስሏት ስጠችው በትንንሽ እጀቹ እንቡ ላይ አማተበ ዶቄቱ ሞልቱ ፈሰሰ ዳግመኛ የቅቤ የዘይት ማስቀመጫ ማድጋዎች ላይ በተመሳሰይ አማተበ ሞልቶ ፈሰሰ ቤቱ በበርከት ተትረፈርፈ የቅዱስ ሚካኤልን ዝክሩን አዘከርች አገሬውን ጠርታ መገበች ለተቸገሩትም አብዝታ ስጠች ይህ በረከት ሁለቱም እስኪሞቱ ድርስ አላለቀም ይላል ገድላቸው፡፡

አባታችን በ 99 ዓመት ከ10 ወረ ከ10 ቀን በዚህ ምድር ኖረው ነሐሴ 24 ቀን አረፈዋል፡፡

ከቅዱሱ አባታችን ረድኤት በረከት ያሳትፈን፡፡
አሜን

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

02 Jan, 07:12


ታህሳስ 24 - የታላቁ አባት አቡነ ተክለሃይማኖት ልደት
🌿🌿🌿🌿🌿🌿
👇👇👇👇👇

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

02 Jan, 07:09


የኢትዮጵያ ክብር እስካሁን በቸርነቱ ተጠብቆ ኖሯል ። ለዚህ ሁሉ ጉልበቲቱ ቤተ ክርስቲያን ናት እንጂ ሰው አይደለም። ኢትዮጵያን በትከሻዋ ተሸክማ የኖረች፤ ዛሬ ልጆቿ ያጠቋት የናቋት የረገጧት ቤተ ክርስቲያን ናት እንጂ ሌላ አይደለችም ይህቺው ናት። ይህም ታሪክ የሚያውቀው እውነት ነው።

ዓለምን ሲያስቸግር የነበረው ኢትዮጵያን ተጋፍቷል ግን አልቻለም፤ አላሸነፋትም። ጣሊያን ፣ ግብፅ፣ ደርቡሽ ያላንበረከኳት "ታላቂቱ ኢትዮጵያ" ተብላ የኖረችበት ጉልበቱ የቤተ ክርስቲያን ነው። ያውም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉልበት ነው። በዚህም ብርሃን ኢትዮጵያ ተጠብቃ ኖራለች።

እንደ ድሮው መስቀል ይዘው፣ ፅና ይዘው፣ ጸሎት አስይዘው በመሃል ተገኝተው የሚያስታርቁ ካህናት አሉ ማለት አልችልም። ትልቁም አሳፋሪው ነገር ይኸው ነው ። ከጳጳሳቱ እስከ ካህናቱ ድረስ እግዚአብሔርን የዘነጉ፣ ክብራቸውን የተዉ፣ አገራቸውን የጠሉ ዐመፀኞች በመሆናቸው ምክንያት ሕዝቡን እርስ በርስ ሲጋጭ እያዩ ምንም የማይመስላቸው።

ይህቺን ሀገር አጥፍቶ ሌላ ከመውረስ ተቻችሎ ሀገርን የራስ ከማድረግ የትኛው ነው የሚሻለው?

ታላቁ ሊቅ ክቡር አለቃ አያሌው ከተናገሩት።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

02 Jan, 07:03


...እንደ ድሮው መስቀል ይዘው፣ ፅና ይዘው፣ ጸሎት አስይዘው በመሃል ተገኝተው የሚያስታርቁ ካህናት አሉ ማለት አልችልም። ትልቁም አሳፋሪው ነገር ይኸው ነው ። ከጳጳሳቱ እስከ ካህናቱ ድረስ እግዚአብሔርን የዘነጉ፣ ክብራቸውን የተዉ፣ አገራቸውን የጠሉ ዐመፀኞች በመሆናቸው ምክንያት ሕዝቡን እርስ በርስ ሲጋጭ እያዩ ምንም የማይመስላቸው።

ይህቺን ሀገር አጥፍቶ ሌላ ከመውረስ ተቻችሎ ሀገርን የራስ ከማድረግ የትኛው ነው የሚሻለው???

..."የኢትዮጵያ ክብር እስካሁን በቸርነቱ ተጠብቆ ኖሯል ። ለዚህ ሁሉ ጉልበቲቱ ቤተ ክርስቲያን ናት እንጂ ሰው አይደለም። ኢትዮጵያን በትከሻዋ ተሸክማ የኖረች፤ ዛሬ ልጆቿ ያጠቋት የናቋት የረገጧት ቤተ ክርስቲያን ናት እንጂ ሌላ አይደለችም ይህቺው ናት። ይህም ታሪክ የሚያውቀው እውነት ነው።

ዓለምን ሲያስቸግር የነበረው ኢትዮጵያን ተጋፍቷል ግን አልቻለም፤ አላሸነፋትም። ጣሊያን ፣ ግብፅ፣ ደርቡሽ ያላንበረከኳት "ታላቂቱ ኢትዮጵያ" ተብላ የኖረችበት ጉልበቱ የቤተ ክርስቲያን ነው። ያውም የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ጉልበት ነው። በዚህም ብርሃን ኢትዮጵያ ተጠብቃ ኖራለች።"

ታላቁ ሊቅ አለቃ አያሌው ታምሩ ከተናገሩት።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

31 Dec, 07:27


˙ •❀• [ ስንክሳር ዘታኅሣሥ ፳፪ ] •❀•

•• ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት ••
๏-❀-๏

በዚች ቀን የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ዳህና በሚባል አገርም ቤተ ክርስቲያኑ የተሠራችበት ተአምራትም ያሳየበትና በዚች ቀን ቤተ ክርስቲያኒቱ የከበረችበት ነው።

የዚያች አገር ኤጲስቆጶስ አርኬላዎስ ምስክር የሆነበት ነው።

ይህም መልአክ ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ምሥጢር የታመነ ሆኖ ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተላከ፦

"የደስታ መገኛ ደስ ይበልሽ! ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነው። አንቺም ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ" አላት።

ስለ መጥምቁ ዮሐንስ መወለድም ካህኑን ዘካርያስን ያበሠረው እርሱ ነው። ይህ መልአክ እጅግ የከበረ የተመረጠ ገናና የሆነ ነውና ስለ እኛ ወደ እግዚአብሔር ይማልድ ዘንድ ልባችንን አንጽተን ወደዚህ የከበረ መልአክ እየለመንን መታሰቢያውን ልናደርግ ይገባል።

🍀🍀

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

06 Dec, 07:38


............#_አንተ_ግን_መድኃኔዓለም_መጠጊያዬ_ነህ
ከአመጸኛ ትውልድ ኖኅን፣ ከሰዶም ምድር ሎጥን፣ ከግብጽ እስራኤልን፣ ከሞት ደብዳቤ ሕይወትን፣ ከአሳ አጥማጅነት ሰው አጥማጅነትን፣ ከሳኦል ጳውሎስን ስትፈጥር አይቻለሁና .......እባክህ በበደል ከጨለመ ፊቴ ብርሃንን፣ በጥላቻ ከታወረ ልቤ ፍቅርን፣ ወደ ክፉ ከሚሮጥ እግሬ መረጋጋትን ፍጠርልኝ። መቼም ለክፉ የተዘጋጀን ለበጎ አድርጎ መሥራት ልማድህ ነውና እኔንም በበጎ ዓላማ አሰልፈኝ። ጌታ ሆይ፥ አምሽቼ ብመጣም የቸርነትህን ዋጋ አታሳጣኝምና፣
#ከእኔ_ኃጢአት_ከአንተ_ምሕረት_አይጠፋምና፣ ስለ ሠራሁት ኃጢአት ሳትፈርድ የቸርነትህን እና የይቅርታህን ሥራ ሥራልኝ።

አቤቱ መጠጊያዬ መድኃኒዓለም ሆይ፥ አንተ በቃልህ ❝ወደ እኔ የመጣውን ከቶ ወደ ውጭ አልጥለውም፤❞ ብለሃልና ወደ አንተ የመጣሁትን እኔን እባክህ አትጣለኝ።🙏🤍

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

06 Dec, 07:36


"እንዲገባኝና እንድለወጥ ራሴንም እንዳስተካክል አንዲት የፀጋ ጠብታ ብትሆንም እባክህ ጌታ ሆይ አፍስስብኝ።

ስጦታህ ነፍሴን ብርህት ካላደረጋት ቸልተኛነቴንና ሥርዓት አልበኝነቴን ያመጡብኝን ፈተናዎች ማየት አልችልምና።"

ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

05 Dec, 14:42


👆👆👆👆👆

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

05 Dec, 14:40


https://telegra.ph/%E1%8B%A8%E1%8A%A0%E1%88%9D%E1%8A%83-%E1%8A%A2%E1%8B%A8%E1%88%B1%E1%88%B5-%E1%8C%88%E1%89%A5%E1%88%A8-%E1%8B%AE%E1%88%90%E1%8A%95%E1%88%B5-%E1%88%88%E1%8A%A0%E1%88%AB%E1%89%B0%E1%8A%9B-%E1%8C%8A%E1%8B%9C-%E1%8A%A0%E1%8C%AD%E1%88%AD-%E1%8B%A8%E1%8C%BD%E1%88%91%E1%8D%8D-%E1%88%98%E1%88%8D%E1%8A%A5%E1%8A%AD%E1%89%B5-%E1%89%A0%E1%89%B0%E1%88%88%E1%8B%AD-%E1%8B%B0%E1%8C%8D%E1%88%9E-%E1%88%88%E1%88%9E%E1%8A%99-%E1%8A%A0%E1%88%9B%E1%88%AB%E1%8A%93-%E1%88%88%E1%8B%88%E1%88%AC%E1%8A%9B%E1%8B%8D-%E1%8A%AD%E1%88%AD%E1%88%B5%E1%89%B2%E1%8B%AB%E1%8A%95-%E1%88%81%E1%88%89-12-05

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

03 Dec, 11:39


አባታችን ተክለ ሃይማኖት ሲናገሩ ‹‹…ከዚህ በኋላ መልአኩ ወደ ሰማይ አውጥቶ ከመጋረጃው ውስጥ አስገብቶ ከሥላሴ ዙፋን ፊት አቆመኝና ሰገድኩለት፡፡ ከዚያ አስቀድሞ በማላውቀው በሌላ ምስጋና አመሰገንኩት፡፡ ‹ተክለ ሃይማኖት ክፍልህ ከ24ቱ ካህናቶቼ ጋር ይሁን› የሚል ቃል ከዙፋኑ ውስጥ ወጣ፡፡ የወርቅ ጽና አምጥተው ሰጡኝና ከእነርሱ ጋር አንድነት አጠንሁ፡፡ ምስጋናዬ ከምስጋናቸው ጋር ልብሴም እንደልብሳቸው ሆነ፡፡ ፈጣሪዬንም በሦስትነቱ ተገልጦ አየሁት፡፡ በጸሎትህ የሚታመን ሰው ሁሉ ስለአንተ ይድናል አለኝ…..››
የአባታችን በረከታቸው ይደርብን! ጸሎታቸው ያስምረን!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

01 Dec, 08:02


የእህታችን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ
21/3/2017

👉 ከዚህ  ደብዳቤ  ጋር  በልዑል  ፊት  ከከበሩት  ዋና  ዋና  ሊቃነ  መላእክቶች  ---  ሊቀ  መላእክት  ቅዱስ  ሚካኤል፣ ሊቃነ  መላእክት  ቅዱስ  ገብርኤል፣  ሊቃነ  መላእክት  ቅዱስ  ሩፋኤል  ትእዛዙንና  ውሳኔውን  ለመፈጸም  በኃያል ሙላት ተነቃንቀዋል።

👉 የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ
ተጻፈ በ7/5/2012 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

01 Dec, 08:02


የወንድማችን ገብረ ማርያም እጅግ ድንቅ ምስክርነት።
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = አዲስአበባ
21/03/2017 ዓ.ም

👉 እንግዲህ ከጠረጋው ቁጣ ማን ይተርፋል? ማንስ ወደትንሣኤው ዘመን ይሻገራል? ግልጽ ነው ደግሜ እላለሁ ለአውሬው ያልሰገደ ምልክቱንም ያልወሰደ ያላመለከ ተሻጋሪ ነው። ኃብትንም እውቀትንም ጉልበትንም ማምለክ ሌላው የአውሬው አምልኮትም እንደሆነ እንወቅ።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ ዘጠነኛ መልእክት ገጽ 6 የተወሰደ
ተጻፈ ታህሳስ 21 2013 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

01 Dec, 08:02


ኢየሱስ ክርስቶስ ካህኑ ለዓለም ንጉሠ ፅዮን ወንጉሠ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ
ድንግል ማርያም እሙ ወእምነ ንግሥተ ፅዮን ወንግሥተ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ

🥢 ዓለሙን ስለ ክፋታቸው ክፉዎቹንም ስለ በደላቸው እቀጣለሁ የትዕቢተኛዎችንም ኵራት አዋርዳለሁ።
ትንቢተ ኢሳያስ 13፡11

በ 21/3/2017 ድንቃ ድንቅ አስተማሪ ምስክርነት ይለቀቃል 👇👇👇

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

01 Dec, 08:02


የወንድማችን ገብረ ሥላሴ እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ናዝሬት
21/3/2017
ክፍል ፩

👉 ጊዜ  የለም  አብቅቷል  መሽቶባችኋል።  አሁን  ከፊታችሁ  ሁሉም  ነገር  ተጭኖ  መጥቷል።  መግቢያ  የለም። መደበቂያ በፍጹም የለም አበቃ!!

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ ዘጠነኛ መልእክት ገጽ 47የተወሰደ
ተጻፈ ታህሳስ 21 2013 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

01 Dec, 08:02


የወንድማችን ገብረ ሥላሴ እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ናዝሬት
21/3/2017
ክፍል ፪

👉 በዚህም  መሰረት  ለወዳጆቻቸው በየግንባራቸው  ላይ  ምልክት  ተደርጓል  ፡፡  ይህንን  የሚያዩት  ለቁጣው  ጠረጋ  እሳት  ለብሰው  እሳት  ጎርሰው  ምድርን እያንቀጠቀጡ  የሚመጡት  ቀሳፊ  መላእክት  መቅሰፍትን  ያዘሉ  ፍርድና  ትእዛዝ  ፈፃሚዎች  ተግባር  ላይ  ሆነው  ያለ  ምሕረት ምልክት  አልባ  የሆኑትን  እንደተፈረደባቸው  እንደተወሰነባቸው  እንደታዘዘባቸው  የአፈፃፀም  እርምጃ  ሲያከናውኑ  ሲያዩ  ብቻ ነው  ፡፡  በጊዜውና  በሰአቱ  የታዘዙበትን  ሲፈፅሙ  ብትጮህ  ብትለምን  እንባህን  እንደጎርፍ  ብታፈስ  ደምም  ብታነባ  እሚሰማህ የለም  ቀሳፊዎቹ  የመጡት  የአምላካቸውን  ትእዛዝ  ለመፈፀም  ተግባራዊ  ለማድረግ  እንጂ  ሊማለዱ  ሊያማልዱ  አይደለም  ፡፡

👉 ከኢትዮጵያ  የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት በአብርሃሙ ሥላሴ ፈቃድ የወጣ                                                መልእክት አስር ገጽ 30 የተወሰደ
ተጻፈ 7/5/2015 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

01 Dec, 08:02


የወንድማችን ሰይፈ ሚካኤል እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = አዲስ አበባ
21/3/2017

👉 ወገኖቼ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! አዎን የእግዚአብሔር ቤተሰቦች! የኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች! እንዲሁም ይህን መልእክትም ሆነ የቀደሙትን ሰባት መልእክታት ለመስማት ዕድሉ የገጠማችሁ፥ ይህን ታላቅ ምሥጢር የእግዚአብሔርን እውነት ለመገንዘብ የሚያስችል ልቡና ይስጣችሁ! መቼም እግዚአብሔር ልቡናችሁን ካላበራው የቀደመው እባብ ሐሰተኛው ነቢይ ዘንዶው ያላደነቆረው፣ ወደራሱም ያላካተተው የአዳም ዘር የለምና! ጥቂቶቹ በእግዚአብሔር የተወደዳችሁ የተመረጣችሁ የከበራችሁ ታላቁን መከራ የታገሳችሁ ልትፅናኑ ይገባችኋል። ዛሬ ቀናችሁ ሊሆን ነውና! ብርሃናችሁ ሊበራ ድካማችሁ ሊታይ ሸክማችሁ ሊራገፍ መድኃኔዓለም ሊክሳችሁ ነውና! አመስግኑ!

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ ዘጠነኛ መልእክት ገጽ 9 የተወሰደ
ተጻፈ ታህሳስ 21 2013 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

01 Dec, 08:02


የእህታችን ምፅላለ መድህን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = አዲስ አበባ
21/3/2017

👉 ሰባቱም መላእክት የቁጣውን ፅዋ ሁሉ ሊያፈሱት በፍጥነት ወደ ምድራችን ገሰገሱ። እንግዲህ ወዴት መሸሸግ ይቻልሃል? የመከርነው የዘከርነው የጮህነው ከዚህ እቶን ላይ ወድቀህ ከነዘር ማንዘርህ እንዳትጠፋ ነበር፤ አልሆነም! እኔም ምናምንቴው በፊቱ የታመንሁ የሥላሴ ባሪያ ለ15 ዓመታት ጮኬ ለፍልፌ አቅሜን ሁሉ ጨረስኩ ዛሬ የምነግርህ የሥላሴ ብርቱ ትእዛዝ ሆኖብኝ እንጂ ዳግም ወደእናንተ መድረስ አልሞክረውም ነበር። ስለ አባቴ ፍቅር ስለአባታዊ ትእዛዙ ስል ስለእናቴ ድንግል ስል መርዶህን እነግርሃለሁ።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ ዘጠነኛ መልእክት ገጽ 6 የተወሰደ
ተጻፈ ታህሳስ 21 2013 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Nov, 07:38


+++++ ዛቲ ይዕቲ ምዕራፍየ ለአለም+++++

እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፤ ይህች ለዘለዓለም ማረፊያዬ ናት /ዛቲ ይዕቲ ምዕራፍየ ለአለም/ መርጫታለሁና በእርሷም አድራለሁ መዝ 131:13።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Nov, 07:03


ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በዉጪ ስላሉ ኢትዮጵያዉያን!!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Nov, 07:02


ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በዉጪ ስላሉ ኢትዮጵያዉያን!!
በዉጪ በስደት ያላችሁ ወገኖቻችን አገራችሁን እየወደዳችሁ በችግር የሄዳችሁ የችግር ምልክት የሆነዉን ዜግነታችሁን ያልጣላችሁ ያልለወጣችሁ የፈጣሪዬና የምዩ ልጆች ጊዜዉ ስለመሸ እራሳችሁን እንደ ሎጥ ከሰዶም ከተማ ለማስመለጥ ከፈጣሪአችሁ ጋር በብርቱ ተነጋገሩ፤ እመቤቴን ጠይቁ፤ ጊዜም አታጥፉ! አጥፊዉ በመላዉ አለም በሁሉም ስፍራ ታዞ በደጅ ቆሞአልና!!

የአገራችሁ ትንሳኤ እነሆ እንደ ፀሀይ ሊያበራ ነዉ፡፡ የምዩ ልጆች እውነተኛ ተዋህዶ ኦርቶዶክሶች አይዞአችህ አምላካችሁ ደርሶአል፡፡ በደጅም ቆሞአል ራሳችሁን አዘጋጁ ጊዜ የለም! አትዘናጉ ተፈጽሞአል፡፡ በሌላ አኩአያ ኢትዮጵያዊ የነበርክ ኢትዮጵያዊነትህን
የናቅህ ዜግነትህን የለወጥህ ለፍርፋሪ የሸጥህ ብኩርናውን ለምስር ወጥ እንደ ሸጠዉ ኤሳዉ ክብርህንና ብኩርናህን ለለወጥህ ምንዝርናን የለመድህ ከአህያ የዋለች ጊደር ፈስ ትማራለች እንደተባለ ምንዝርናን፣ ዉሸትን፣ ንቀትን፣ስስትን፣የተማርክ ተዋህዶ
እምነትህን ንቀህ ከፈረንጅና ከአረብ እምነት የቃረምክና የተቀበልክ፣ መንገድህ ያድንህ፣ ያመንክበት ይከልልህ ለካቶሊኩም፣ ለፕሮቴስታንቱም፣ ለእስላሙም፣ ለሂንዱም፣ ለቡዲሂዝሙም ተከታይ ሁሉ የሚጠብቀው ሁሉ ላንተም ይጠብቅሃል ተዝጋጅተህ ጠብቅ!!
ህዝቅኤል ምእ ፡ 14 ፡ 12 – 20 ዘጸአት ምእ ፡ 12 ፡ 21 - 28
ኢሳኢያስ ምእ ፡ 40 ፡ 6 - 8 ኢሳኢያስ ምእ ፡ 57 ፡ 11 - 13

ከሊቅ እስከ ደቂቅ ላለህ ወገኔ በሙሉ!!
ሁሉም የሚመዘንበት የሚዳኝበት፣ የሚለይበት፣ ሰአት ተፈጽሞአል የሚቀረው ስንዴውን ወደ ጎተራ እንክርዳዱን ለእሳት
መስጠት ብቻ ነዉ፡፡ ሽማግሌ ባልቴት፣ ጎልማሳ ጎልማሲት፣ ወጣት ሴት ወንድ ሁልህም ልብና ኩላሊትን በሚመረምር አምላክ
ተለይተሃል! ለምህረት የተጻፈዉ በግንባሩ ምልክት በስውር ተደርጎበታል፡፡ ምህረትን የማያገኘዉ (ለእሳት የተጻፈው) ምልክት አልባ ነው፡፡

በስውር የታተመው ምልክት የጨበጥህና ያልጨበጥህ መሆንህን የሚለዩህ ቅዱሳን መላእክት ስለሚያውቁህ! የሌለውን
ለእሳት ያለውን ወደእረፍትና ወደምህረት የምታውቀው ደግሞ ስትድን ከመአቱ ስትተርፍ ብቻ ነው፡፡ መዳንህንም በዚህ
ታረጋግጣለህ፡፡ ከአጠገብህ ያለችው ያለው ሲሸኙ ምልክት አልባ መሆናቸዉን ታዉቃለህ ትረዳለህ፡፡
እኔ መሪ ነኝ፣ እኔ ሚኒስቴር ነኝ ፣እኔ የእምነት መሪ ነኝ፣ የጦር አለቃ ነኝ፣ ባለኒዩክለርም፣ ባለጠብመንጃ ብትሆን የአለም
መሪም ሁን፣ የአጥፊዉ ጋሻ ጃግሬ ስለነበርክ፣ አለቃና ምንዝር ስለሆንክ፣ የዘር ሹመኛ ተጠቃሚ፣ የዘር ፈራጅ ስለነበርክ ምንም ከምንም የሚያድንህ የለም፡፡ ሁሉም የአለም ገጽታ በሙሉ በሞት ይፈተሻል፡፡ የሚያድንህ የልብህ ቅንነት እምነትህና ስራህ ብቻ ነዉ፡፡
የሰበሰብከዉ ሃብት፣ ንብረት፣ በምህረት ለታሰቡት ይቀራል፡፡ አንተ እንደዘራኸው ታጭዳለህ፣ ፈጣሪህን …. እንደ አምላክ
ቆጥረህ የተከለልከዉ በዘረኛ ገዢ ጉያ ነው፡፡ እሱ ስለሚሄድ አንተስ ወዴት ትቀራለህ!! አብረህ ትጓዛለህ፡፡ የአህያ ባል ከጅብ
አያስጥልም እንደሚባለው ለሆድህም ሆነ ላመንክበት አላማ ያዉ ከሃዲ የእግዚአብሄር አገር የወገን ጠላትነህ፤ ስለሆነም ስፍራህ
መቃብር ብቻ ነው፡፡ እንደ ስራህ መጠን ይከፈልሃል፡፡የማንም ገዢ አያመልጥም፡፡ ራሱንም ሆነ አንተንም አያድንም፡፡ ስለዚህ ከፊትህ
የመጣዉን የፈጣሪ በትር ሳያበጥር እንደማይመለስ ተረድተህ ታጥቀህ ጠብቅ! የታዘዘዉ አጥፊህ በየደጅህ ቆሞአልና፡፡
ይህንን መልእክት ስታነብ እንደለመድከው የስጋ ብልጠትና የፖለቲካ ክህሎት ያዋጣኛል ብለህ እንዳታስብ፡፡ መከራህም
ከሚያከብደው በቀር የሚፈይደዉ የለም፡፡
አለም ገና ከእንቅልፉ አልነቃም፤ በመጣበትም ቁጣ ፈጽሞ አልደነገጠም ሁሌም እንደሚያስበዉ በእዉቀት በእረዳ ተረዳዳ
በገንዘብ እወጣዋለሁ ብሎ ያምናል፡፡

በምድር መንቀጥቀጥ፣ በጎርፍ፣ በማእበል፣ በሙቀት፣ በረሃብ ሲመታ ኮንፈረንስ ያደራጃል፣ ሳይንሳዊ ዘዴ ይተልማል፣
የእርዳታ ድርጅት ይሰይማል ደረስኩ ይላል፡፡ ይሄ ሁሉ ይቆማል አይረዳም ለራሱ የሚሰጠዉን ካራና በትር ስለማይቋቋም አንዱ ላንዱ
የሚረዳዳበት ወቅት ይጠፋል፡፡ ሁሉም እንደ ስራው በመጣው ጥፋት ይጠረጋል፡፡ እንደ ጪስም ይተናል፡፡ ምድራችን እዉነትን
በማያዉቁ አመጸኞችና ወንጀለኞች የዲያቢሎስ ልጆች ስለተሞላች በግድ መጽዳት አለባት፡፡ ለቅዱሳንም የተመቻች የበረከት ምድር
ልትሆን ይገባል! ስለሆነም ይኸዉ የፈጣሪ ፈቃድ ይፈጸማል፡፡
በኢትዮጵያ የሚደርሰው የሚፈጸመው ሁሉ እነሆ ይመጣል! እግዚአብሄር የቀባቸው በምድሪቱ ላይ ሲነግሱ ያኔ ብቻ
የእረፍት ጅማሮ ይሆናል፡፡ ይህ እስኪሆን ግን አለም አይታ የማታውቀውን ጥፋትና ውድመት ታስተናግዳለች በዚህን ጊዜ ሁሉም
የሚጮኸው የፈጣሪ ቁጣ እንዲቆምለት ብቻ ነው፡፡ ያ ደግሞ የሚሆነው የታዘዘው ሁሉ ሲፈጸም የእግዚአብሄርም ህዝቦች ነጻ ሲወጡ
ብቻ ነው፡፡

የታመኑ የፈጣሪ ልጆች በአለም ሁሉ ፊት የሚያበራውን ከጌታ የተሰጣቸውን ስልጣን ሲያጸኑ! ሁሉም ሲንበረከክና በፈጣሪና
ላከበራቸው ሲገዛ ብቻ ነው! ሰላም፣ በረከት፣ ቸርነት፣የሚሆነው ይኸው ሲሆን ብቻ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከብዙ ጉዳት በህዋላ የሚፈጸም
ነው፡፡ ምክንያቱም የሰው ልጅ ትእቢቱንና አውቃለሁ ባይነቱን ቶሎ አይጥልምና!! አለም ሁሉ በታላቅ እንባና ጩኸት ይሞላል፡፡
ከቁጣው ብርታት የተነሳ አለም ያለፈች እስኪመስል ድረስ ፤ አሁንም ደግሜ እለዋለሁ! በኢትዮጵያና በዙረያዋ ባሉ ተራሮች (ሀገሮች)
ሁሉ የብርሃን ዙፋኑን የሚዘረጋው ጌታ ልጆቹን ከዙፋኑ ላይ ሲያስቀምጥ ብቻ ነው መስከን የሚጀምረው ከዚህ ውጪ
የሚመጣ አንዳችም ነገር የለም፡፡

እግዚአብሄር ለምህረት ያሰባቸው ክርስቲያን ሆኑ እስላም ሆኑ ካቶሊክ ሆኑ ሌላም ሆኑ ድርጅት ውስጥም ኖሩ አልኖሩ
እምነት ይኑራቸው አይኑራቸው፤ ብቻ ልባቸው ቅን የዋህ ትሁትና ደግ ከሆኑ እውነትን የሚወዱ ከሆነና ፈጣሪን የሚፈልጉ ይሁኑ እንጂ!
አምነውና ተጠምቀው በብርሃናዊቷ ተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጅነት ተባርከው በብርሃን ጎዳና ይገሰግሳሉ! የምህረትንም ዘመን ያያሉ
#ቶ #ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን
#source:-https://www.facebook.com/Ethiopia-ye-alem-birhan-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB-%E1%8B%A8%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D-%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83%E1%8A%95-103272261088123/?ref=bookmarks

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Nov, 07:01


የኢትዮጵያ ትንሳኤ!!
/ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን/

ወገኔ የኢትዮጵያ ህዝብ በፈጣሪህ እጅግ የተወደድክ ህዝብ እኮ ነህ እጅግ ላከበራት ለእናቱ ለእናታችን ለድንግል ማርያም
ልጅ አድርጎ የሰጠህ ለማንም ያልሰጠውን በረከትና ህይወት ያዘዘልህ እኮ ነህ!! የእምዩ (የድንግል) ልጆች ለመሆኑ እንዲህ ለወደዳችሁ
አምላክ ምን ትከፍላላችሁ!! አለምን ሁሉ ለእናንተ እንዲገዛ እንዲታዘዝ ወሰነ፡፡ እስቲ ወገኔ አስተውል! ያለፉት ለዚች የተባረከች ምድር የደከሙት አባቶቻችንን ድካም ለ 7000 (ሰባት ሺ) ዘመን ሲመዝን፣ ሲለካ፣ሲመዘግብ ኖሮ ቃሉን በፍጹም የማያጥፍ ጌታ ለኔና ላንተ ላንቺ ብድራትን ሊከፍል መጣ!! ለመሆኑ ምንስ ትከፍለዋለህ!! ጌታ ሌላ አይጠይቅም ከልብህ የሚመነጨውን ምስጋና ብቻ ነው፡፡
በፈጣሪ ፊት ያለህን ክብር አላወከውም! አሁን ግን ልታውቀው ይገባሃል፡፡ በስራህ አይደለም የወደደህ አያት ቅድመ አያቶችህ በእምነታቸው ቆመው በጸጋው ያፈሱት በረከት ነው፡፡ ለዚህም የትንሳኤ ዘመን ያደረሰህ የታመነ አምላካችን ሁሌም የታመነ
ነው፡፡ ከቃሉ የሚጨመር የሚቀነስ የለም፡፡

አድምጥ ደስም ይበልህ!! በአለም የሚያበራ ክብር ለኢትዮጵያ ተሰቶአታል!! በበረከቱና በቸርነቱ በፍጹም ፍቅሩም
የምትሞላው ኢትዮጵያ በእመቤቴ የእናትነት እቅፍ እና በረከት ታኖርሃለች፡፡ ከእንግዲህ አገርህ ኢትዮጵያ ወደውርደት አትመለስም
ለበረከት የታደልከው ወገኔ እንደ አሁኑ ክፉ ትውልድ ፈጣሪህን እንዳታስከፋው እነግርሃለሁ፡፡ አሁን ቁጣውንም ጥፋቱንም ታየዋለህና
ከፈጣሪህ ፈቀቅ እንዳትል ከዚህ ጥፋት በኃዋላ በበረከቱና በቸርነቱ ብዛት ደስታህ እጅግ ስለሚበዛ በስጋ ምቾት ተጠልፈህ ከፍቅሩና
ከቸረህ ጸጋው እንዳትኮበልል ተጠንቀቅ!!
የተባረከው ወገኔ አንተ መልካሙን ታያለህ ልጆችህም እንዲያዩና ለትውልድ እንዲያዘልቁ አብረን ታምነንና ለአምላካችን
ቃልና ትእዛዙ ተግተን አገራችን በፈጣሪ ፊት እንደታመንች፣ እንደተወደደች፣ እንድትዘልቅ የሚያደርገውን ስራ እንስራ!!
በፍቅሩ ኑሩ የሚጠላውን ጥላ፣ የሚወደውን ውደድ አሁን የምታየውን ዲያቢሎስ የዘራውን አመጽና የጥፋት አዝመራ ከምድርህ አጥፋ፣ እውነትን ብቻ አንግስ፡፡

ሙሴ በእስራኤላውያን ክህደት ሲበሳጭ እግዚአብሄር ያለውን ልታስብ ይገባሃል፡፡ ጌታእንዲህ ነበር ያለው፣ ሙሴ ባሪያው ይህንን ልቡ ጠማማ ህዝብ ላጥፋው ተወኝ አንተንም ለታላቅ ህዝብ መሪ ላድርግህ ነው ያለው፣ ያታላቅ ህዝብ ደግሞ የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፡፡ ሙሴ አስተዳደርን የተማረው ከኢትዮጵያዊው የሚስቱ አባት ከዮቶር ነበር፡፡ ኢትዮጵያበህገ ልቦና፣ በህገ ኦሪት፣ ዛሬም በህገ ወንጌል ያለውን ስርአት ሳታፋልስ ትውፊቱን ጠብቃ መጥታለች፡፡ እግዚአብሄር አምላካችን በባሮቹ በኩል ያስተላለፈውን ቅዱስ ቃሉን፣ በጥንቃቄ ጠብቃ ላንተ ለዛሬው ትውልድ አድርሳለች፡፡ ሌላው የናቀውን የጣለውን የደለዘውን የቀነሰውን ተግባር ሳትከተል በትክክል እንደነበር እንደቃሉ ጠብቃ አኑራለች፡፡ ከአለም ሁሉ በሚለየው የእምነት ስርአትዋ ዛሬም ሁሌም እንደ ጠል በሚንጠባጠብና እንደ ምንጭ ውሃ በሚንቆረቆር ዜማዋ
ፈጣሪን ታመሰግናለች፡፡

ታላላቅ መሪዎችን እግዚአብሄር ሰጥቶአት ነበር፡፡ እነ ካሌብን፣ እነ ኢዛናን፣እነ አብርሃ ወአጽብሃ፣ እነላሊበላን እነ
ዘርአያእቆብን ወዘተ… በእምነቱም በስጋውም አገዛዛቸው የገነኑትን አሳልፋለች፡፡ ግዛትዋም እጅግ የሰፋና እስከ የመን የዘለቀ ነበር፡፡
በየዘመኑ የተነሱ ጠላቶች ሲቀንስዋት ሲሸርፍዋት መጡ፣ መሪዎቹም በታሪክ እያነሱ መጡ፣ የቅርቡን ብናነሳ ከዘመነ መሳፈንት ጀምሮ
በኢትዮጵያ ታሪክ በድንበር ጉዳይ ብዙ የተወሳሰበ ሁኔታ ተፈጥሮና እስከዘሬ ተወሳስቦ እንደቀጠለ እናያለን፡፡ በታሪክ ያነሱና
አገራቸውን እየሸረፉ ለጠላት በመስጠት ለስልጣናቸው መደላደል ብቻ የሚደክሙ መሪዎች እነሆ ቆመን እያየን ነው! የታሪክ ድንኽነት
ፈጽሞ የማያማቸው ናቸው፡፡
ይሁንና ወገኔ አትጨነቅበት ጠላት በየአቅጣጫው በቃኘው በነደፈው አካሄድ ሁሉ ኢትዮጵያን ከምድረ ገጽ አጥፍቶአል፡፡
ዛሬም የሚችለውን እያደረገ ነው፡፡ ይሁንና ፈጣሪ ሁለንተናዊ ጥበቃ ስላደረገ እዚህ ደርሳለች፡፡

ከአሁን በህዋላ ግን ይህ ታሪክ ይቀየራል፡፡ ሃፍረትም መሸማቀቅም ለጠላቶች ይሆናል፡፡ የጠበበው የተሸረፈው ወደነበረበት
ብቻ ሳይሆን እጅግ በማትገምተው ሁኔታ ሰፍቶ ይንሰራፋል፡፡ በነካሌብ ዘመን የነበረው ብቻ ሳይሆን ከዚያም በላይ ይሆናል፡፡ ወገኔ!
ይግረምህ አምላክህ ይህንን ያደርጋል፤ ከዚህም አልፎ የሌሎች አገሮች ሁሉ እድልና እጣፈንታ በሙሉ የሚወሰነው እዚህ በታላቋ
ኢትዮጵያ ይሆናል፡፡ አለምም የኢትዮጵያ ምርኮና በረከት ይሆናል፡፡
መዝሙር ዳዊት 36 ( 37 ) 9 ትንቢተ ሶፎኒያስ ምእራፍ 3
ኢሳኢያስ ምእራፍ 57 ኢሳኢያስ ምእ 62 ፡ 1 - 5
መዝሙር ዳዊት 57 ( 58 ) መዝሙር ዳዊት 56

ወገኔ ልብ ብለህ አስተውል ፈጣሪህ ለክብሩ ሊመሰገንበት በእውነት ወዶሃል ቅን ፍርዱንም እንደጸሃይ ሊያወጣ ወስኗል፡፡
ስለዚህም እኔ ወንድምህ የምመክርህን ታናሽ ምክር አድምጥ!!
ለሰው ልጅ ሁሉ ፍቅር ይኑርህ ክፋትን፣ ጭካኔን፣ ስስትን፣ ምንዝርናን፣ ሌብነትን፣ መልካም ያልሆነውን ሁሉ ፈጽሞ ከራስህ
አርቅ በእምነት ወንድምህ እህትህ ለሆኑ ለአገርህም መታመን ይኑርህ ከዚህ ሁሉ በላይ ፈጣሪ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም
ሃሳብህ በፍጹም ነፍስህ ውደደው!!!
#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን #ቶ

#source:-https://www.facebook.com/Ethiopia-ye-alem-birhan-%E1%8A%A2%E1%89%B5%E1%8B%AE%E1%8C%B5%E1%8B%AB-%E1%8B%A8%E1%8B%93%E1%88%88%E1%88%9D-%E1%89%A5%E1%88%AD%E1%88%83%E1%8A%95-103272261088123/?ref=bookmarks

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Nov, 07:01


የኢትዮጵያ ትንሳኤ!!
/ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን/

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Nov, 06:58


ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ በራእዩ “በሰማይ ያለችው የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ተከፈተች፡፡ በውስጧም ያለችው ታቦተ ሕግ ታየች” /ራእይ. 11፥19/ በማለት የተናገረውን
ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በመጽሐፈ አክሲማሮስ ሲተረጉመው “በሥላሴ ጸዳል በሥላሴ ብርሃን የተመላች ስመ ሥላሴ የተጻፈባት ታቦት በኢየሩሳሌም ሰማያዊት አለች፡፡ በዚህች ታቦት ላይ ከፍጥረተ ዓለም በፊት ስመ እግዝእትነ ማርያም ተጽፎባት ነበር፡፡ ቅድመ ዓለም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከመፈጠሯ በፊት በአምላክ ኅሊና ታስባ ትኖረ ነበር የሚለው መሠረቱ ይህ ነው” ብሏል፡፡
#እንኳን_አደረሳችሁ_አደረሰን።
#ኢትዮጵያ #ጽዮን

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Nov, 06:43


✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ እንኩዋን ለኃያል ሰማዕት "ማር ቴዎድሮስ" እና "ቅዱስ አንያኖስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+"+ ቅዱስ ቴዎድሮስ ማር ሰማዕት +"+

=>በቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ የሆነው ማር ቴዎድሮስ የተወለደው በምድረ አንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ ክ/ዘ ነው:: አባቱ ዮሐንስ በትውልድ ግብጻዊ የሆነ ክርስቲያን ነው:: እናቱ ግን አስቸጋሪና ጣዖት አምላኪ ሶርያዊት ነበረች::

+ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ ሚስት ባሏ ክርስቲያን መሆኑን አታውቅም ነበር:: ቴዎድሮስ (የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው) በተወለደ ጊዜ ግን ጠብ ተነሳ:: እሱ ክርስትና ለማስነሳት: ሚስት ደግሞ ወደ ጣዖት ቤት ለመውሰድ ተጋጩ:: ሚስት ወገኖቿ ባለስልጣኖች ናቸውና ልጁን ቀምታ ባሏን ዮሐንስን ወደ ግብፅ አሳደደችው::

+ዮሐንስ በስደት ባለበት ሃገር ስለ ልጁ ፈጽሞ ይጸልይ: ያለቅስም ገባ:: እግዚአብሔር ደግሞ ልመናውን ሰማ:: ማር ቴዎድሮስ ወጣት በሆነ ጊዜ ማንም ሳይጠራው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔዶ ተማረ: ተጠመቀ:: ዕለት ዕለትም ጾምና ጸሎትን ከምጽዋት ጋር ያበዛ: ድንግልናውን ለመጠበቅ ይተጋ ነበር::

+በዛው ልክ ደግሞ ገና በ20 ዓመቱ በጉልበቱ ኃያል: በውበቱም ደመ ግቡ: በጠባዩም ገራገር ነበርና ተወዳጅ ነበር:: ነገሥታቱም የአንጾኪያ የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ሾሙት:: እነሆ እስከ ዛሬ "የሠራዊት አለቃ" ተብሎ ይጠራል::

+ማር ቴዎድሮስ በተሳተፈባቸው ጦርነቶች ሁሉ ተሸንፎ አያውቅም:: ይልቁኑ የነገሥታቱን (የጠላት) ልጆች በመማረክ ነው የሚታወቀው:: እንዲያውም አንድ ጊዜ ከአሕዛብ ጋር በተደረገ ጦርነት ብቻውን አሸንፏቸዋል::

+የፋርስ ሰዎች ሊዋጉ ሲመጡ መልአክ ከሰማይ ወርዶ ሰይፍ ሰጠው:: ፋርሶችን "በከንቱ ከምትጠፉ ወደ ሃገራችሁ ተመለሱ" አላቸው:: እነርሱ ግን ተሳለቁበት:: ከፈረሱ ወርዶ ወደ ምስራቅ ዙሮ ጸልዮ በመስቀል አማተበ:: በመካከላቸው ገብቶም በመልአኩ ሰይፍ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር አጠፋቸው::

+አንድ ቀን ወደ አንድ ከተማ ቢገባ ዘንዶ ሲመለክ አገኘ:: ይባስ ብሎ የአንዲት ክርስቲያን ልጆችን ለመስዋዕትነት ሲያቀርበቧቸው ተመለከተ:: በስመ ሥላሴ አማትቦ: በፈረሱ ላይም ተቀምጦ ዘንዶውን በጦር ገደለው:: የዘንዶውም ርዝመት 24 ክንድ ነበር::

+ከነገር ሁሉ በሁዋላ ቅዱስ ቴዎድሮስ ስለ አባቱ ወሬ ሰምቶ: ካለበት ሥፍራ አፈላልጎ አግኝቶ ደስ አሰኘው:: እስኪያርፍ አብሮት ቆይቶ: ቀብሮት ወደ አንጾኪያ ሲመለስ ግን የሚያሳዝን ነገር ጠበቀው::

+ክርስቶስ ተክዶ: ጣዖት ቁሞ: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለው: የክርስቲያኖች ደም ፈሶ: ከተማዋ በግፍ ተሞልታ ተመለከተ:: እርሱም በዚያች ሰዓት መወሰን ነበረበትና አደረገው:: የሁሉ ሠራዊት አለቃ ቢሆንም የክብር ልብሱን አውልቆ: ባጭር ታጥቆ በንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ፊት ቆመ::

+ማር ቴዎድሮስ በአደባባይ እንዲህ ተናገረ:- "አንሰ አመልኮ ለክርስቶስ ንጉሠ ስብሐት በኩሉ ልብየ: ወእሠውዕ ሎቱ - እኔስ የክብር ባለቤት ክርስቶስን በፍጹም ልቤ አመልከዋለሁ: ለእርሱም ብቻ እሠዋለሁ::" ንጉሡ በቁጣ መሬት ላይ ጥለው እንዲደበድቡት አዘዘ:: ወታደሮቹ ደሙ እስኪንጠፈጠፍ ገረፉት::

+በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃይተው በእሳት አቃጠሉት:: እርሱ ግን በጸሎቱ እሳቱን ውሃ አደረገው:: ወታደሮቹ እርሱን በብዙ አሰቃዩ:: እርሱ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ጸና: ታገሠ::

+በመጨረሻም ጌታችን በግርማ ወርዶ "ወዳጄ ቴዎድሮስ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ: ገድልህን (ዜናህን) የጻፈ: ያጻፈ: ያነበበ: ገዝቶ በቤቱ ውስጥ ያኖረውን ሁሉ
እምርልሃለሁ" አለው::

+በስሙም ረድኤት እንደሚደረግ ነግሮት ዐረገ:: ወታደሮቹም በዚህ ቀን አንገቱን ሰይፈው የክብር አክሊልን ተቀብሏል:: እጅግ ብዙ ሺህ ሰዎችም አብረውት ተሰይፈዋል::

+"+ ቅዱስ አንያኖስ ዘግብጽ +"+

=>ይህ ቅዱስ አባት ውለታው ከፍ ያለ ነውና በምድረ ግብጽ እጅግ ይከበራል:: በተለይ ክርስትናን ከሐዋርያት ተቀብሎ ለምዕመናን ያስረከበ አባት በመሆኑ ልዩ ቦታ ይሰጠዋል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

+ወንጌላዊው ሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስ በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ተመድቦ: በፈቃደ እግዚአብሔር ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ በ50ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ወደ ምድረ ግብጽ ወረደ::

+እስክንድርያ ከተማ በሜዲትራኒያን ባሕር ዳርቻ እንደ መኖሯም መጀመሪያ ወደ እርሷ ደረሰ:: ልክ ወደ ከተማ ሲገባ ገና አንደበቱ ለወንጌል ሳይከፈት እንቅፋት መትቶት ጫማው ተበጠሰ:: ያን ሁሉ በርሃ የቻለች ጫማ በእንቅፋት በመበጠሷ እያዘነ ወደ ጫማ ሰፊ ዘንድ ደርሶ "ሥራልኝ?" ይለዋል::

+ይህ ጫማ ሰፊ አንያኖስ (አንያኑ) ይባላል:: ጣዖት አምላኪ: ግን ደግሞ ቅንና ገር የሆነ ሰው ነበር:: "እሺ" ብሎ ሲሰፋለት መሳፈቻው (መስፊያው) ስቶ መሐል እጣቱን ስለ ወጋው "ኢታስታኦስ (አታኦስ)" ብሎ ጮኸ:: ትርጉሙም "አንድ አምላክ" ማለት ነበር::

+ይህንን የሰማው ቅዱስ ማርቆስ ቀና ብሎ "ጌታየ ሆይ! ጐዳናየን ስላቀናህልኝ አመሰግንሃለሁ!" ብሎ: ምራቁን እትፍ ብሎ በጭቃ የአንያኖስን እጅ ቀባው::

+ወዲያውም ደሙ ቁሞ: ቁስሉም ድኖ እንደ ነበረው ሆነ:: በዚህ ተአምር ድንጋጤም: ደስታም ቢሰማው "ማነህ አንተ?" ሲል ቅዱሱን ጠየቀው:: ወንጌላዊውም መልሶ "እኔ የክርስቶስ ሐዋርያ ነኝ" አለው::

+አንያኖስም "እባክህ ወደ ቤቴ እንሒድ" ብሎ ሐዋርያውን ጋበዘው::
እቤት ሲደርሱም ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር አስተናግደውት የሕይወትን ቃል ለመኑት:: ቅዱስ ማርቆስም ከስነ ፍጥረት እስከ ጌታችን የማዳን ሥራ አስተምሯቸው አመኑ:: አጥምቆ ሥጋውን ደሙን አቀበላቸው::

+ይህቺው የቅዱስ አንያኖስ ቤትም በምድረ ግብጽ የመጀመሪያዋ ጉባኤ ቤትና ቤተ ክርስቲያን ሆነች:: ቅዱሱ ሐዋርያ በ60 ዓ/ም አካባቢ በቅዱስ አንያኑ ቤት ሆኖ በርካቶችን አሳመነ:: በሰማዕትነት ከማረፉ በፊትም ቅዱስ አንያኖስን የምድረ ግብጽ ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) አድርጐ ሾመው::

+ቅዱስ አንያኖስም ለ12 ዓመታት የክርስቶስን መንጋ እያበዛ ተጋደለ:: ከሐዋርያው የተቀበለውን ንጹሕ ዘር ዘራ:: የድኅነት የምሥራቹንም አዳረሰ:: ይሔው ይህ መልካም ተክል ዛሬም ድረስ ሳይጠወልግ አለ::

+የአሁኑ ፓትርያርክ አቡነ ታውድሮስም ከቅዱስ ማርቆስ 118ኛ ሲሆኑ ከቅዱስ አንያኖስ 117ኛ ናቸው:: ቅዱሱ ለእኛ ኢትዮዽያውያንም የክህነት አባታችን ነው:: ይህች ቀንም ዕለተ ዕረፍቱ ናት::

=>አምላከ ቅዱሳን ክፉውን አርቆ ከበጐው ዘመን ያድርሰን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን::

=>ኅዳር 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ማር ቴዎድሮስ ኃያል ሰማዕት
2.ቅዱስ አንያኖስ (አንያኑ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት

=>+"+ በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኩዋ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ:: ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ: አትናወጡም:: ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: +"+ (1ዼጥ. 3:13)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Nov, 06:43


✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ እንኩዋን ለኃያል ሰማዕት "ማር ቴዎድሮስ" እና "ቅዱስ አንያኖስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

28 Nov, 08:57


የዚህ ዘመን ኢትዮጵያን ወደ ትንሳኤዋ የሚያሻግራት አብሳሪው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ ለምኑት፣ ዘክሩት፡፡

ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር።
ኢትዮጵያ ርስተ ድነግል ማርያም።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን።
ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዥ።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

27 Nov, 11:47


ከባድ በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በ500 ሄክታር ላይ የተዘራ የደረሰ ሰብልን አወደመ

በአማራ ክልል ደባርቅ ከተማ አሥተዳደር የገጠር ቀበሌዎች በጣለው ከባድ በረዶ ምክንያት ሰብላቸው ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ለከፋ ችግር መጋለጣቸውን አርሶ አደሮች ተናግረዋል።

ኅዳር 14/2017 ዓ.ም ከቀኑ ስምንት ሰዓት ጀምሮ ለ30 ደቂቃ የጣለው ከባድ በረዶ የቀላቀለ ዝናብ በሶስት ቀበሌዎች ከ500 ሄክታር መሬት በላይ የደረሱ ሰብሎች ላይ ጉዳት አድርሷል።

ጉዳቱ በተለያዩ የሰብል አይነቶች ላይ የደረሰ ሲሆን ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍና ጥራጥሬ ሰብሎች ይገኙበታል።

አርሶ አደሮቹም በአካባቢው ባሕል መሰረት ሰብላቸውን በደቦ ለመሰብሰብ ነገ ዛሬ በሚሉበት ወቅት ድንገት የጣለው በረዶ ሰብላቸውን ሙሉ በሙሉ እንዳወደመባቸው ተናግረዋል።

አቶ ራራ ደሴ የተባሉ የጉዳቱ ሰለባ የሆኑ አርሶ አደር በደረሰው ጉዳት በማዘንና በመደናገጥ በርካታ አርሶ አደሮች ለከፋ የጤና ቀውስ መዳረጋቸውን አንስተዋል።

"ጉዳቱ ያልተጠበቀ ነው፤ እንኳን እኛ እንስሳቱ ራሱ የሚበሉት ድርቆሽ ሳር አልተረፈም" ሲሉ አርሶ አደሩ ማሬ ታረቀኝ ለአሚኮ ተናግረዋል።

የሰሜን ጎንደር ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ባለሙያው ጥላሁን ዓለም ለአሚኮ እንደገለጹት ከ600 በላይ አርሶ አደሮች ጉዳት ደርሶባቸዋል። በፍጥነት መልሶ የማቋቋም ሥራ መሠራት እንዳለበትም ጠቁመዋል።

የደረሰው ጉዳት ከባድ በመኾኑ አርሶ አደሮችን መልሶ የማቋቋም ሥራ በመሥራት በበጋ መስኖ ሰብል ልማት ምርቱን እንዲያካክሱ ለማድረግ ጥረት እንደሚደረግ የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር ግብርና ጽሕፈት ቤት ኀላፊ በዕውቀት አየነው ተናግረዋል።

በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦችም ሆኑ ግብረ ሰናይ ድርጅቶች አርሶ አደሮችን መልሶ በማቋቋም ሥራው ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪ ቀርቧል።

Via አሚኮ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

26 Nov, 07:02


#ሰማእቱ_ቅዱስ_እስጢፋኖስ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

26 Nov, 07:02


#ሰማእቱ_ቅዱስ_እስጢፋኖስ

በስመ #አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን አምላካችን መድኃኒታችን #ኢየሱስ_ክርስቶስን በሰማእቱ ስም ለምናመሰግንበት #ለቅዱስ_እስጢፋኖስ ወርሐዊ መታሠቢያ ክብረ በአል እንኳን አደረሰን

የትውልድ ሀገሩ #ኢየሩሳሌም ሲሆን አባቱ ስምዖን እናቱ ደግሞ ማርያም ትባላለች ዘመኑም የመጀመሪያው ምእተ ዓመት ነው

እንግዲህ በዘመነ ሐዋሪያት የማዕዱን እና የውስጡን አገልግሎት እንዲያስተናብሩ መንፈስ እና ጥበብ የሞላባቸው ሰባት ሰዎች ተመርጠው በሐዋሪያት አንብሮተ እድ ሆነው ከተሾሙት ከሰባቱ ዲያቆናት መካከል በቅድስና ሕይወቱ ለክርስቲያኖች አብነት የሆነው ሰማዕቱ #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ይገኝበታል እስጢፋኖስ የሚለው ቃል የግሪክ ቃል ሲሆን ትርጉሙም #አክሊል ማለት ነው

መፅሐፍ ቅዱስን ወደ ግእዝ በኋላም ወደ አማርኛ የመለሱት አባቶች በቀጥታ የግሪኩን እስጢፋኖስ የሚለውን ቃል ተጠቅመዋል #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ምንም እንኳን ስሙ የግሪክ ስም ይሁን እንጂ በትውልዱ አይሁዳዊ ነው

ወላጆቹ ይህንን ስም የሰጡት ተብሎ የሚታመነዉ ወላጆቹ በፍልስጤም ጠረፋማ ከተሞች ይኖሩ ስለ ነበር የግሪክ ባሕልና ቋንቋ ተጽእኖ አድሮባቸው ይሆናል ተብሎ ይገመታል

#ቅዱስ_እስጢፋኖስ በሐዋርያት ጥበቃ የነበረችውን ቤተ ክርስቲያን ከአምላክ ዘንድ ባገኘው የማስተማርና የፈውስ ሀብት ያገለግል ነበር በእርሱም ታላላቅ ተአምራት ይፈፀሙ ነበር

ስለዚህም ሕዝቡ ከፊት ይልቅ እጅግ እየበዛና በትምህርት እየጠነከረ መጣ አይሁድም ይህን ተመልክተው በቅዱስ #እስጢፋኖስ ላይ በቅናትና በጠላትነት ተነሡበት ነገር ግን ከመንፈስ ቅዱስ ባገኘው ጥበብና ኃይል እነርሱን በቃልም በድርጊትም ይቃወማቸው ነበርና ሊረቱት አልተቻላቸውም

ስለዚህም #እግዚአብሔርን ሙሴን ሲሳደብ ሰምተነዋል ሙሴ የሠራልንን ሥርዐት ይለውጣል በዚህ ቤተ መቅደስና በሕጉ ላይ የስድብን ቃል ይናገራል ይህንንም ቤተ መቅደስ የናዝሬቱ ኢየሱስ አፍርሱ ብሎአል እያለ ያስተምራል እያሉ ሕዝቡን ሽማግሌዎችንና ፀሐፍትን በማናደድ ይዘው ከሸንጎ ፊት አቆሙት

ቅዱስ #እስጢፋኖስን በሸንጎ ፊት ባቆሙት ጊዜም ፊቱ ልክ እንደ #መልአክ ፊት ሆኖ በርቶ ነበር እርሱም ለተከሰሰበት ነጥብ መልስ ሰጠ ከአብርሃም እስከ ክርስቶስ ለእነርሱ የተሰጣቸውን በረከት በመቃወማቸው ከተስፋ ቃል እርቀው እንደተወገዱ ገለጠላቸው

#ክርስቶስንም ባለመቀበላቸው ወቀሳቸው በዚህም ምክንያት በቁጣ ተነሣስተው ከከተማ ውጭ በመውሰድ በድንጋይ ወግረው ገደሉት #ቅዱስ_እስጢፋኖስ አይሁድ በድንጋይ እየወገሩት ሳለ ሰማያት ተከፍተው #ክርስቶስን በአብ ቀኝ ቆሞ ተመለከተ ይህንን ራእይ የክርስቶስን ትንሣኤን ለማይቀበሉት አይሁድ አሰምቶ ተናገረ

እነርሱ ከፊት ይልቅ በእርሱ ጨከኑ በድንጋይም ወገሩት ነገር ግን #ቅዱስ_እስጢፋኖስ ጌታውን ክርስቶስን መስሎ ነበርና ልክ እንደ መምህሩ #አቤቱ_ይህን_ኃጢአት_አትቁጠርባቸው” ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኾ ነፍሱን ሰጠ በቤተክርስቲያንም ታሪክ ስለ ክርስቶስ መስክሮ ሰማዕትነትን የተቀበለ የመጀመሪያው ዲያቆን ሆኖአል

በደማስቆ መንገድ ላይ ክርስቲያኖችን ያሳድድ የነበረ ሳውል በኋላም ቅዱስ ጳውሎስ ተብሎ ስያሜ የተሰጠው ሐዋርያ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ በሚወግሩበት ወቅት በእርሱ ሞት ተስማምቶና ድንጋይን በእስጢፋኖስ ላይ ያነሡትን የአይሁድ ልብስ ይጠብቅ የነበረ ብላቴና ነበር

ነገር ግን #ቅዱስ_ጳውሎስ ሐዋርያ ከሆነ በኋላ የሰማእቱ #የእስጢፋኖስን ቤተሰቦች አጥምቆአቸዋል ይህ ደግሞ ድንቅ ነው በቤተክርስቲያን መፅሐፈ ስንክሳር የበዓላት ዝርዝር ላይ የመታሰቢያ ቀን በመስጠት ይከበራል

በጥቅምት "17" ቀን የድቁና ማዕረግን በአንብሮተ ዕድ በሐዋርያት የተቀበለበትን፣ ጥር "1" ደግሞ የእረፍቱ መታሰቢያ ሆኖ ይከበራል፣በየወሩ በ "17" የሰማእቱ መታሠቢያም ነው በረከቱ ምልጃና ፀሎቱ አይለየን "አሜን" ✝️ 💒 ✝️

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

25 Nov, 07:57


#ኅዳር_16

አንድ አምላክ በሚሆን #በአብ_በወልድ_በመንፈስ_ቅዱስ ስም በእግዚአብሔር አንድነት #ሰኞ #ቀን #የሚነበብ #የኪዳነ #ምሕረት #ድርሳን ይህ ነው። 🙏

ልመናዋ ክብሯ ለዘለዓለሙ ከሁላችን ጋር ይደርብን አሜን።
ማርያምን በመረጣት በእግዚአብሔር አብ ስም፣ በማሕፀኗ ባደረ በእግዚአብሔር ወልድ ስም፣ ባጸናት በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ስም የእመቤታችን የቃል ኪዳንዋን መጽሐፍ እንጀምራለን።

ከእርሱ ጋር በባለሟልነት ትኖር ዘንድ ያከበራት ያነገሳት፣ እርሷ በኅሊናዋም በሰውነቷም ድንግል ስትሆን ከዚህ ዓለም ወደ ሰማይ ያሳረጋት፣ በዚህች ዐውደ ምሕረት የምንሰግድለት የማሕፀኗ ፍሬ የካህናት አለቃ ኢየሱስ ክርስቶስ ኀጢአታችንን ለዘለዓለሙ ይቅር ይበለን አሜን። 🙏

#በዚህች_በበዓሏ_ቀን_የሚነበብ_የኪዳነ_ምሕረት_ድርሳን_ይህ_ነው። 🙏

የሕይወት እናት ድርሳን፣ የመድኃኒት እናት ድርሳን፣ ያቸናፊ እግዚአብሔር እናት ድርሳን፣ የአካላዊ ቃል እናት ድርሳን ይህ ነዉ ።

ይህችውም የሲኦል ማዕበል ሞገድ በተነሣ ጊዜ የማትነዋወጥ የሃይማኖት አምድ ናት። የማትፈርስ የአድማስ ግድግዳ እርሷ ናት። አማኑኤልን የወለደችው እርሷ ናት፤ የምሥራች ማደሪያ በመስቀል የታጀበች ምስጋናዋ የተወደደላት እርሷ ናት። 🙏

#ቅዱሳን_ከሲኦል_የሚሻገሩባት_መርከብ_እርሷ_ናት። #የፋና_መብራት_እርሷ_ናት። 🙏

ይህች ድንግል በምን ትመሰላለች? ዓመታት ሳይፈጠሩ ወራት ሳይቆጠሩ በልዑል እግዚአብሔር ኅሊና ነበረች። የተዘጋጀች ምድር እርሷ ናት። ከ ፍጡራን አስቀድማ የነበረች መላእክት የሚያመሰግንዋት ፀሐይ የከለላት ሁለተኛ ሰማይ እርሷ ናት። 🙏

መጀመሪያና መሠረት ይህች ናት። የአባታችን የአዳም የድኅነት ተስፋ እርሷ ናት። የአቤል መዓዛ መሥዋዕት የአባታችን የኖኅ የእምነት ቃል ኪዳን መሸጋገሪያ መርከብ እርሷ ናት። የቅዱሳን ጥበብ የሲራክ መጽሐፍ፣ የኤልያስ የሠርክ መሥዋዕት የባሮክ በለስ የሄኖክ ራዕይ አምላክን የወለደች እመቤታችን ማርያም ይህች ናት። 🙏

የኖኅ ድኅነት፣ ስምንቱን ነፍሳት ከጥፋት ውሃ የሠወረች፣ የሰማይ አምላክ የቃል ኪዳኑ ምልክት የምትሆን፣ ብሩህ ቀስተ ደመና የተባለች ማርያም ይህች ናት። 🙏

የሰማያዊ ክርስቶስ ማደሪያ ይህች ናት፤ አንዲቱስ ስንኳን የማትሻር ዐሥሩ ቃላት የተጻፉባት የሙሴ ጽላት ይህች ናት። 🙏

የሮቤል ተክል፣ የይሳኮር የልደቱ ምልክት፣ የአሴር የእህል በረከት፣ የአስቴር ጸሎቷን የምታሳርግ፣ ሆለሆርኒስን ድል የምትነሣ ለዮዲት ጥበብ የምትሆን ማርያም ይህች ናት። 🙏

የይሁዳ የምስፍናው ሀብት፣ የዛብሎን የኅሊናው ተስፋ፣ የሶስናን ልብ ከኀዘን የምታረጋጋ፣ የኢያቄምና የሐና ልጅ፣ የዮሐንስ የአንደበቱ ክብር ሶልያና የተባለች ማርያም ይህች ናት። 🙏

የሴም የርስቱ ምድር፣ ምሥራቃዊት የኤዶም ገነት፣ ከነገደ ካም ኃጢአትን የምታስተሠሪ፣ የንፍታሌም ዘንባባ፣ የብንያም የሠርክ ምግብ፣ እስራኤልን ከመከራ ምድር ያወጣች፣ የለመለመ መናን በመመገብ የሚጣፍጥ ውሃን በማጠጣት በምድረ በዳ የጠበቀቻቸው፣ በኤፍሬምና በምናሴ መካከል አንድነትን የምታደርግ የኢያቄምና የሐና ልጅ ማርያም ይህች ናት። 🙏

#ልመናዋ_ክብሯ_ለዘለዓለሙ_ከሁላችን_ጋር_ይኑር_አሜን 🙏

#ምንጭ፦
#ድርሳነ_ኪዳነ_ምሕረት፣ ገጽ 117 – 119፣ ቁጥር 1 – 19፣ 2001 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

23 Nov, 11:21


የእኔ ዓላማ ኢትዮጵያውያን ሁሉ አገራቸው ኢትዮጵያ ከማንኛውም የዓለም አህጉር የማታንስ፡ ይልቁንም በሃይማኖት የምትበልጥ፡ እነሱም ከማንም የማያንሱ ይልቁንም የሥነ ጽሕፈት፡ የባህል ፡የትምህርት፡የሕግ፡የቋንቋ ፡ የፊደል፡የእኩልነትና የባላገርነት ነባር ታሪክ ያላቸው በመሆናቸው የሚያስመካ እጅግ በጣም ከፍ ያለ ነባር ታሪክ ያላቸው የማይጠፉ የሕይወት ቅርስ ባለቤቶች ባለ መብቶች መሆናቸውን ለማስረዳት ብቻ ነው፡፡

ኢትዮጵያውያን ሁሉ ኢትዮጵያ አገራቸው ፡እግዚአብሔር አምላካቸው ልዩ ምልክቶቻቸው ስለሆኑ ሳይፈሩና ሳያፍሩ ቀጥ ብለው መቆም፡ በትክክል ማየት፡ ማሰብ፡ማለም የሚቻላቸው ስለሆኑ እንግዲህ በመብታቸውና በእምነታቸው ተመርኩዘው አንድነታቸውን አጽንተው መኖር ይገባቸዋል፡፡ ክብራቸው ከአምላካቸው ፡ ከሀገራቸው የተገኘ ስለሆነ የራሳቸው የግላቸው ነው ለማንም አይሰጥም የሌላ ክብርም አያስፈልጋቸውም፡፡

ታላቁ ሊቅ ክቡር
አለቃ አያሌው ታምሩ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

22 Nov, 13:52


https://youtu.be/7ot1xNp42nA

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

21 Nov, 08:16


‹‹ዞብል››
#ዞብል_ታማኝ_ለጌታዉ_የተባለዉ_የንጉስ_ፋሲለደስ_ፈረስ፡፡
ኢትዩጵያ ከቱርክ ጋር በ1640ዎቹ መግቢያ ባደረገቸዉ ጦርነት ወቅት የንጉስ ፋሲለደስ ፈረስ ዞብል ታሪክ ፡፡

ንጉስ ፋሲለደስ ግርማ ሞገሱ የሚያምርና ጠንካራ ፈረስ ነበረቸዉ ፤ይህ ፈረስ ዞብል በመባል ይጠራል፡፡ ንጉሱ ለዚህ ፈረስ የነበራቸዉ ፍቅር በጣም የተለየ እንደነበረ ታሪካዊ፣ ባህላዊ መረጃዎችና ትዉፊቶች ያመለክታሉ፡፡ ለፈረሱ ንጉሱ ራሳቸዉ ምግብ ያቀርቡለታል ፤ በአገልጋዩቹ ሲታጠብም እራሳቸዉ ይገኙ ነበር፡፡ የሚገርመዉ ይህ ፈረስ ሲሞት ንጉሱ ከቤተሰባቸዉ አንድ ሰዉ የሞተ ያህል እንዳዘኑ እና የተለየ የመቃብር ቦታ አዘጋጅተዉ እንዳስቀበሩት ይነገራል፡፡ አሁንም ይህ የዞብል መቃብር ቦታ በንጉሱ መዋኛ ገንዳ ጎን ይገኛል፡፡

ታዲያ ይህ ፈረስ ሃገራችን ከቱርክ ወረራ እራሷን በምትከላከልበት ወቅት የዚህ ፈረስ ለጌታዉ ታማኝነቱ ያሳየ አስደናቂ ገድል ፈፅሟል፡፡ የቱርክ ጦር የሃገራችን ደንበር ተሸግሮ ወደ መተማና ቋራ ለመዉረር በተዘጋጀበት ወቅት ንጉሱ የሃገራቸዉን ዳር ደንበር በማስከበር ኃላፊነታቸዉን ተወጥተዋል፡፡ ታዲያ በአንድ ወቅት ንጉሱ ከቱርኮች ሲከላከሉ በወቅቱ የተደራጀ ሰራዊትና ትጥቅ የነበረዉ የቱርክ ጦር የንጉስ ፋሲለደስን ጦር በተወሰነ መልኩ አሸንፎ ንጉሱ ይማረካሉ፡፡ ንጉስ ፋሲለደስን የማረከዉ የቱርክ ጦር ንጉሱን ከነፈረሳቸዉ ወደ ቱርክ ጦር ካምፕ ወስዶ ያስራል፡፡ የቱርክ የጦር መሪዎችም በንጉሱ መማረክ ተደስተዉ በአሻጋሪ የሚያዩት ቀሪዉን የንጉስ ፋሲለደስ ጦር አሸንፈዉ የኢትዩጵያ ግዛት ለመዉረር መቋመጥ ያዙ፡፡ በቱርክ የጦር ካምፕ ላይ ሌላዉም ደስታ ለጦር መሪዎች የፈጠረዉ ባለግርማ ሞገሱና ጠንካራዉ ዞብል በእጃቸዉ መሆኑ ነበር፡፡ ታዲያ እነዚህ የቱርክ የጦር መሪዎች ጎበዝ የተባሉ ቱርካዊያን ፈረስ ጋላቢዎች እየመረጡ ዞብልን ለማስጋለብና ለማላመድ ቢሞክሩም ዞብል ሁሉን ከመሬት እየጣለ ያፈርጣቸዉ ጀመር፡፡ በጣም የሚደንቀዉ ነገር ዞብልን መጋለብ ቀርቶ ቀርቦ ገመድ ለመያዝ ኮረቻ ለማስቀመጥ የሚደፍር ጠፋ ፡፡ ዞብል በኃላ እግሮቹ እየተራገጠና አንገቱን እያወራጨ ለምንከስ በመሞከሩ ማንም ደፍሮ መቅረብ አልቻለም፡፡

በፈረሱ ኃይለኛነት የተገረሙት የቱርክ የጦር መሪዎች ስለምን ንጉስ ፋሲለደስን ጠርተን ፈረሱን አያላምድልንም በማለት ወስነዉ ንጉሱ ከታሰሩበት ጠርተዉ ዞብልን በጦር ካምፓቸዉ ክልል ብቻ ፈትተዉ እንዲጋልቡት ያዟቸዋል፡፡ ዞብል ንጉሱን ፋሲለደስን ሲያይ መጮህ ጀመረ ንጉስ ፋሲለደስም ከልጀነቱ ጀምረዉ ቀልበዉ ፤ተንከባክበዉ ፤አግባብተዉ ያሳደጉትን ታማኙን ፈረሳቸዉን ዞብል ሽምጥ ጋልበዉ ከቱርክ የጦር ካምፕ በመዉጣት ደንበሩን ተሻግረ ወደ ወገን ጦር ተቀላቀሉ፡፡ በንጉሱ (በኢትዩጵያ) የጦር ሰፈር ዉስጥ ሌሊቱን በሙሉ ሲጨፈር ሲሸለል አደረ፡፤ ሁሉም በዞብል ታማኝነት ተገረመ፡፡ በበነጋታዉም በንጉሳቸዉ መመለስ ሞራላቸዉ ተገነባዉ የኢትዩጵያ ጦር የቱርክን ጦር በማሸነፍ ዳር ድንበሩን አስከበረ፡፡

=> የዞብል መቃብር በክብ ቅርጽ በቅምብብ የተሰራ መታሰቢያ ሲሆን ከቆይታ ብዛት ጉዳት እየደረሰበትና ዛፎች በመካከሉ እየበቀሉበት እየፈረሰ ያለ ምናልባት ብቸኛው የኢትዮጵያ ፈረስ መዘክር ነው።

የመረጃ ምንጭ፡-የጎንደር ጠቅላይ ግዛት ታሪክና ባህል ገጽ የተገኘ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

18 Nov, 08:16


የሶስት ሜትር ርዝመት ያለው "የጥፋት ቀን አሳ" ተብሎ የሚጠራው ዓሳ በካሊፎርኒያ የባህር ዳርቻ ላይ ተገኝቷል -

በሦስት ወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ነው በካሊፎርኒያ የታየው

ይሄ ዓሳ እንደ የመሬት መንቀጥቀጥ ወይም ሱናሚ ያሉ የተፈጥሮ አደጋዎችን ጠሪ ነው ይባላል::

እ.ኤ.አ. በ 2011 ከእነዚህ ዓሦች ውስጥ 20 የሚሆኑት በጃፓን የተገኙ ሲሆን ብዙም ሳይቆይ በታሪክ ውስጥ በጣም ኃይለኛ ከሆኑት የመሬት መንቀጥቀጦች አንዱ ተከስቶ ነበር::

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

16 Nov, 07:56


#ኢትዮጵያ_የዓለም_ብርሃን መልዕክታት ከኅዳር 7
🟢🟡🔴

እንኳን ለኢትዮጵያ የአለም ብርሀን መልዕክት ህዳር 7 1998 የመጀመሪዋ መልዕክት በአብርሃሙ ሥላሴ ቀን ለአለም የተላከበት ቀን በሰላም በጤና እንቁ የኢትዮጵያ የአለም ብርሃን ቤተሰቦች እንዲሁም ቅን ደግ የዋህ የሆናችሁ የተዋህዶ ኦርቶዶክስ ልጆች አደረሰን አደረሳችሁ። ለኢትዮጵያ ትንሳኤ አጋዝትአለም ሥላሴ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱሳን መላዕክታን ፃድቃን ሰማዕታት ያድርሱን ያድርሳችሁ።
1.1998 ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ተጽፎ የወጡ ለአዳም ዘር በሙሉ! የእግዚአብሔር መልዕክታት 👇

መልዕክት አንድ ፦ይህ የመጀመሪያ የፈጣር ውሳኔ ተብሎ ሊጠቀስ ይችላል። ወይም ቢጫ መብራት የተየበት ሊባል ይችለላ።

1. መልዕክት 1 ኅዳር 7.1.1998 ዓ.ም ተጻፈ።

2.መልዕክት 2 ግንቦት 27.2000.ዓ.ም ተጻፈ።

3.መልዕክት 3 መጋቢት 19.2001 ዓ.ም ተጻፈ።

4.መልዕክት 4 የካቲት 1.6.2002 ዓ.ም ተጻፈ።

5.መልዕክት 5 መስከረም 21.1.2004 ዓ.ም ተጻፈ።

6.መልዕክት 6 ታሣሥ 19.4.2007 ዓ.ም ተጻፈ።

7.መልዕክት 8 ታሣሥ 21.4.2011 ዓ.ም ተጻፈ።

8. ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት ደብዳቤ ጥር 7.5.2012 ዓ.ም ተጻፈ።

9. መልዕክት 9 ታሣሥ
21.4.2013 ዓ.ም ተጻፈ።

10.መልዕክት 10 ጥር 7.5.2015 ዓ.ም ተጻፈ።

ሳይገባንና ሳይገባን በቸርነቱ ብዛት ይህንን ሁሉ ለሰጠን ለልዑል እግዚአብሔር ክብር ምስጋና አምልኮና ውዳሴ ልርሱ ይድረሰው እናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስሟ የተመሰገነ የተከበረ ይሁን ቅዱሳን ሁሉ አምላክ በሰጣቸው ጸጋ ክብር ምስጋና ይድረሳቸው አሜን።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

15 Nov, 06:49


እንኳን ለቊስቋም ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን ።
#ህዳር_ 6
በዚህች ቀን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ከልጇ አንዲሁም ከዮሴፍና ሶሎሜ ጋር 3 ዓመት ከ 6 ወር በስደት ከተንገላታች በኋላ ወደ አገራቸው የተመለሱበት ቀን ነው፤ ከግብጽ ሲመለሱ ጌታችን በእመቤታችን ጀረባ ላይ ሆኖ እነዚያ እውራንን ባበሩ ጣቶቹ ወደ ኢትዮጵያ ይጠቁም ያመለክት ነበር፤ እመቤታችንም ልጄ ሆይ ለምንድነው ጣትህን የምታመለክተው ብትለው "ያቺ የተባረከች አገር ናት እኔን የሚያመልኩ አንቺን የሚማልዱ በፍቅርሽ የነደዱ ቅዱሳን መነኮሳት የሚፈልቁባት አገር ናት፤ ያንቺ ዘመዶች ሰቅለው ይገድሉኛል በዚህች አገር ያሉ ግን ሳይዩኝ ያመኑኛል፤ አስራት በኩራትሽ ትሁን ብሎ ሰጥቷታል፡፡ በኪደተ እግራቸውም ጣና ሐይቅን፤ ዋልድባንና ሌሎችንም ቦታዎች ዞረው እንደባረኩ ድርሳነ ኡራኤልና ተአምረ ማርያም ላይ በስፋት ተጽፏል፡፡
«ድንግል ሆይ ርጉም በሆነ ሄሮድስ ዘመን ከልጅሽ ጋር ከሀገር ሀገር ስትሸሺ ከአንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ ፤
ድንግል ሆይ ከዓይንሸ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ፤
ድንግል ሆይ ረሐቡንና ጥሙን፣ ችግሩንና ሐዘኑን፣ ከእርሱ ጋር የደረሰብሽንም ጭንቅ ሁሉ አሳስቢ››
ቅዳሴ ማርያም
እመቤታችንን ከሐና ማህጸን ፈጥሮ ከፍጥረተ ዓለም ለይቶ ከሁሉ አልቆ የእናት አማላጅ ትሁናችሁ ብሎ የሰጠን እግዚአብሔር ይመስገን።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

14 Nov, 14:50


#ኅዳር_6፤ ደብረ ቊስቋም፤ #እመቤታችን_ከልጇ_ጋርስ_ደትን_የጀመረችበት_ዕለት_ነው፡፡

ድንግል ማርያም ከልጇና ከአረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍ ጋርለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) ከተሰደደች በኋላ #ግንቦት_24_ደግሞ_በዓተ_ግብጽ_ (ወደ ግብጽ ወደ ደብረ ቊስቊም ገብታ ያረፈችበት ቀን ነው፡፡

ዖፍኒ ረከበት ላቲ ቤተ፤ ወፍም ቤቷን ሰራች፡፡ መዝ. ፹፫፥፫
ንጉሥ ተወልዷል መባሉን የሰማው ሔሮድስ 144,000 ሕጻናትን ሲፈጅ በቅዱስ ገብርኤል ትዕዛዝ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አንድ አምላክ ልጇን አዝላ፤ በአንዲት አህያ ላይ ተቀምጣ፤ ጥቂት ስንቅ ቋጥራ፤ ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ስደት ወጣች፡፡ ከገሊላ ተነሥታ በጭንቅ፣ በመከራ፣ በረሃብና በጥም፣ በሐዘንና በድካም፣ በእንባ ተጕዛ በዚህች ቀን ምድረ ግብፅ ገብታ በሥደት እጅግ ብዙ መከራ ተቀብላለች::
† የአምላክ እናቱ እሳትን አዝላ በብርድ ተንገላታለች::
† ለእኛ የሕይወት እንጀራን ተሸክማ እርሷ ተራበች::
† የሕይወትን ውሃ ተሸክማ ተጠማች::
† የሕይወት ልብስን ተሸክማ ተራቆተች::
† የሕይወት ፍስሐን ተሸክማ አዘነች::
† እመ አምላክ ተራበች፣ ተጠማች፣ ታረዘች፣ ደከመች፣አዘነች፣ አለቀሰች፣ እግሯ ደማ፣ ተንገላታች::
ለሚገባው ይሕ ሁሉ የተደረገው ለእኛ ድኅነት ነው:: በእውነት ይህንን እያወቀ ለድንግል ማርያም ክብር የማይሰጥ ሰይጣን ብቻ ነው:: አራዊት: ዕፀዋትና ድንጋዮች እንኳን ለአመላክ እናት ክብር ይሰጣሉ:: አረጋዊው ቅዱስ ዮሴፍና ቅድስት ሰሎሜ ደግሞ የክብር ክብር ይገባቸዋል:: ከአምላክ እናት ከድንግል ማርያምና ከቸር ልጇ ጋር መከራ መቀበልን መርጠዋልና::
#መድኃኔ_ዓለም_ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ_ለምን_ተሰደደ? #ለምን_ስደቱን_ወደ_ግብፅና_ኢትዮዽያ_አደረገ?
1. ፠ትንቢቱን ይፈጽም ዘንድ:: በፈጣን ደመና ወደ ግብፅ እንደሚወርድ ተነግሯልና(ኢሳ 19፥1፣ ዕን. 3፥7)
2. ፠ምሳሌውን ለመፈጸም፤ የሥጋ አባቶቹ እነ አብርሃም፥ ያዕቆብ (እሥራኤል):፥ ኤርምያስ ወደዚያው ተሰደዋልና::
3. ከግብፅ ጣዖት አምልኮን ያጠፋ ዘንድ:: (ኢሳ. 19፥1)
4. የግብፅና የኢትዮዽያ ገዳማትን ይቀድስ ዘንድ::
5. ሰው መሆኑ በአማን (በእውነት) እንጂ ምትሐት እንዳልሆነ ለማጠየቅ:: (ሰው ባይሆን ኑሮ አይሰደድም ነበር:: ሔሮድስ ቢያገኘው ደግሞ ሊገድለው አይችልም:: ያለ ፈቃዱና ያለ ዕለተ ዐርብ ደሙ አይፈስምና::
6. ስደትን ለሰማዕታት ባርኮ ለመስጠት:: እና
7. የአዳምን ስደት በስደቱ ለመካስ ነው::

እመ ብርሃን ድንግል ማርያም ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት (ወይም ለ42 ወራት) (1275 ቀናት) በስደት የቆየችባቸው ቦታዎች አሉ::
፠ በመጀመርያ ድንግል ማርያም ከርጕም ሔሮድስ ስትሸሽ መጀመሪያ የሔደችው ከገሊላ ወደ ሶርያ ደንበር (ደብረ ሊባኖስ) ነበር:: በዚያም የሸሸጋት ቅዱስ ጊጋር መስፍኑ በሔሮድስ ሲገደል ወደ ምድረ ግብጽ ወረደች፡፡
፠ በግብጽም ለብዙ ጊዜ ከአንዱ ወደ ሌላው ስትሸሽ ቆየች:: ‹‹እንዘ ከመ በግዕት ግድፍት አመ ሳኮይኪ ውስተ ምድረ በዳ፡፡›› እንዲል:: (እሴብሕ ጸጋኪ)
፠ ቀጥላም በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ገብታ ደብረ ቢዘን ላይ (አሁን ኤርትራ ውስጥ ነው) ዐረፈች፤
፠ ከደብረ ቢዘን ደብረ ሐዊ፣ በደብረ ዳሞ፣ አኵሱም፣ ደብር ዐባይ፣ ዋልድባ አድርጋ እየባረከች ቆይታለች፤
፠ በዋልባም ቆይታቸው ልጇ ገዳሙን በኢትዮጵያ በብጨኝነት ራሱ የገደመውን ገዳም መሥርቶ እየባረከ ወደ ጣና ሄደዋል፡፡
፠ በጣና ገዳማትም፤ በተለይ በጣና ቂርቆስ ለ100 ቀናት ቆይታ ቀጥታ በጐጃም ወደ ሸዋ ሔዳ ደብረ ሊባኖስን ቀድሳለች::
፠ ቀጥላም እስከ ደብረ ወገግና ደብረ ሐዘሎ ደርሳለች፤ በእግሯ ያልደረሰችባቸውን የሀገራችን ክፍሎች በደመና ተጭና ዐይታ ባርካቸዋለች፡፡
፠ በደብረ ኤረር ተራራ ላይም ከልጇ ኢትዮጵያን በዐሥራትነት ተቀብላለች፡፡
ሔሮድስ መሞቱን መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል የነገራትም እዚሁ ኢትደዮዽያ ውስጥ መሆኑን ትውፊት ያሳያል::
እመቤታችን የሄሮድስን ሞት ከሰማች በኋላ ቊስቋም ከሚባል ተራራ ላይ ሆና ደስታዋን አብረዋት መከራን ከተቀበሉት ከዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር አከበረች፡፡ ከሃገራችን ሰዎች (ከሰብአ ኦፌር) የተቀበለችውን ስንቅና ስጦታ በ5 ግመሎች ጭና ከቅዱሳኑ ዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ኅዳር 6 ቀን ቊስቋም ውስጥ ገብተው ከድካም ዐርፈዋል፤ ሐሴትንም አድርገዋል::
#ግብጽ_ደብረ_ቊስቋም_፤
ከክርስቶስ ስደት 400 ዓመታት በኋላ በዚህች ቀን የግብጿ ደብረ ቊስቋም ታንጻ ተቀድሳለች፤ የቅዱሳን ማደሪያም ሆናለች፡፡ ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ፤ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ390ዎቹ አካባቢ ድንግል እናቱን፣ ቅዱሳን ሐዋርያትን፣ አእላፍ መላእክትን፣ ጻድቃን ሰማዕታትን፣ አስከትሎ ወረደ፡፡ የወቅቱ የግብጽ ፓትርያርክ ቅዱስ ቴዎፍሎስና ሊቁ ቅዱስ ቄርሎስ ቤተ ክርስቲያኑን አንጸው፤ ሕዝቡን ሰብስበው ይጠብቁት ነበርና ወርዶ ቀድሶላቸው ታላቅ ደስታ ኾኗል::
ይህቺ ቀን ለእኛ ለክርስቲያኖች ሁሉ እጅግ የደስታ ቀን ነውና ሐሴትን እናድርግ፤ የሰማይና የምድር ጌታ ለእኛ ሲል ካደረገው ስደቱ ኅዳር 6 ተመልሷልና:: ስደቷን አስበን ካዘንን: መመለሷን አስበን ደስ ልንሰኝ ይገባልና:: ‹‹አብርሒ አብርሒ ናዝሬት ሃገሩ፤ ንጉሥኪ በጽሐ ዘምስለ ማርያም መጾሩ›› ልንልም ይገባል፡፡

ልዑል እግዚአብሔር ይመስገን የእናታችን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን! አሜን!!!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

12 Nov, 08:22


ዓባይን በግዝት!
በዚኽች ዕለት እንደነ ሄኖክና ኤልያስ ከሞት የተሠወረው ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ ከኢትዮጵያ ወጥቶ እንዳይሔድ የዓባይን ወንዝ በጸሎቱ በማቆም ያደረገው ድንቅ ተአምር ይህ ነው፡- ‹‹ግብፃውያን ለአባቱ ለቅዱስ ላሊበላ ለመንግሥቱ እጅ መንሻ ግብር ብዙ ወርቅና ብር እያመጡ ይሰጡት ነበር፡፡ ነገር ግን ቅዱስ ላሊበላ በሕይወት ሳለ መንግሥቱን ለቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ ካወረሰው በኋላ በቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ ዘመን ለኢትዮጵያ መንግሥት ያስለመዱትን እጅ መንሻ ማምጣትን አቋረጡ፡፡ የገድሉን ማማርና ጽድቁን ሳያውቁ እጅ መንሻውንና ግብሩን ከለከሉ፣ ለመንግሥቱም አልተገዙ፡፡ በእርሱም ላይ ያመጹ እነዚህ የግብፅ ሰዎች ከዓባይ ወንዘ ውሃ በቀር ዝናብን አያውቁም፡፡

ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብም የአባቱን ልማድ ስላስቀሩና ክብሩንም ስላቃለሉ 3 ዓመት ከ3 ወር ያህል የዓባይን ወንዝ በጸሎቱ ኃይል አቆመው፡፡ ግብፃዊያንም የሚጠጡትና የሚዘሩበት ውሃን ፈጽመው አጡ፡፡ እህልና ውሃም በማጣት በድርቅ ተመቱ፡፡ ሰዎቻቸውና እንስሶቻቸውም አለቁ፡፡ በዚህም ጊዜ እርስ በእርሳቸው ‹‹…ይህ የከፋ መቅሰፍት ያጋጠመን በምንድነው?›› ብለው ሲመካከሩ በዚያ የሚኖር አንድ ሰው ስሙ ማማስ የሚባል ‹‹ይህች የከፋች መከራ ያገኘችን የዚያን የሕፃኑን የቅዱስ ላሊበላን ልጅ የቅዱስ ነዓኵቶ ለአብን እጅ መንሻውን ስለከለከልነው ለመንግሥቱም ስላልተገዛን ነው›› አላቸው፡፡ ግብፃዊያኑም ‹‹ምን ብናደርግ ከዚህ ረኀብና መከራ እንድናለን?›› አሉት፡፡ ማማስም ‹‹እጅ መንሻውን ስጡ፣ ለመንግሥቱም ተገዙ፣ በከተማውም ውስጥ ገብታችሁ ለፈጣሪው ስገዱ›› አላቸው፡፡ እነርሱም በወርቅ የተለበጡ ልዩ ልዩ ስጦታዎችን የመንግሥቱንም እጅ መንሻ የ6 ዓመቱንም ጨምረው ይዘው ወደ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ መጥተው ሰግደው ስጦታቸውን ሰጥተው ይቅር ይላቸው ዘንድ እያለቀሱ ለመኑት፡፡ እርሱም ‹‹የሠራችሁትን በደላችሁን ክፉ ሥራችሁን ሁሉ እግዚአብሔር ይቅር ይበላችሁ›› አላቸው፡፡ በወንጌል ቃል ጨውነት የጣፈጠ የተባረከ አንደበቱ ይህን በተናገረ ጊዜ ለ3 ዓመት ከ3 ወር ቆሞ የነበረው የዓባይ ወንዝ ከግዝቱ ተፈቶ በሰላም መፍሰስ ጀመረ፡፡ በአገራቸውም ንውጽውጽታ ሆነ፣ ልቅሶአቸውም ወደ ደስታ ተቀየረ፡፡ ረኀብና ችግራቸውም ወደ ጥጋብ ተለወጠ፡፡ ግብፃዊያኑም በቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ በጸሎቱ ኃይል አመኑ፡፡ መንፈስ ቅዱስን የተመላ ዳግማዊ ኤልያስን ሆኖ አግኝተውታልና፡፡

ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ክህነትን ከንግሥና ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አስተባብረው ይዘው ኢትዮጵያን ከመሩ ከአራቱ የዛጉዌ ነገሥታት አንዱ ሲሆን በነገሠበት 40 ዓመት ሙሉ ዓርብ ዓርብ ቀን የክርስቶስን ሕማም እያሰበ በዕንቁና በወርቅ በተሽቆጠቆጠው ዘውዱ ፈንታ የእሾህ አክሊልን ደፍቶና በአምስቱ ቅንዋተ መስቀሎች ምሳሌ አምስት ጦር ዙሪያውን ተክሎ እያለቀሰ ይጸልይና ይሰግድ ነበር፡፡

ጌታችንም በመጨረሻ ለቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ተገልጦለት ‹‹...እውነት እልሃለው 40 ዓመት ሙሉ እንባህን ያፈሰስክባት ይህች ምድር እስከ ዕለተ ምጽአት እያነባች ትኖራለች፣ ይኸውም የእኔን መከራ እያሰብክ ከዐይንህ ዕንባ ሳይቋርጥ እንዳለቀስክልኝ ሁሉ ከቤተ መቅደስህ በእንባ መልክ የሚንጠባጠብ ጠበል ይፍለቅልህ፣ ይህም የዕንባህ ምሳሌ ነው፤ ከዚህ ለሚጠጡ ለሚጠመቁ ድኅነት ይሁናቸው›› የሚል የምሕረት ቃልኪዳን ሰጥቶታል፡፡ ጌታችን ይህን አስገራሚ ቃልኪዳን ከሰጠው በኋላ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብን በሞት ፈንታ እንደነ ሄኖክና ኤልያስ ኅዳር 3 ቀን ሰውሮታል፡፡ በቃልኪዳኑም መሠረት ብዙ ፈውስን የሚሰጠው ጠበሉ ዛሬም ድረስ ልክ እንደሰው ዕንባ ቤተ መቅደሱ ካለበት ዋሻ ላይ እየተንጠባጠበ ወደ ታች ይወርዳል፣ ምንም እንኳን ከዋሻው በላይ ያለው መሬት ሜዳ ቢሆንም ቃልኪዳኑ ነውና የጠበሉ መጠን ክረምት ከበጋ አይጨምርም አይቀንስም፡፡ ይልቁንም በሰው ዕንባ መጠን ጠብ ጠብ እያለ በመውረድ ከእርሱ ለሚጠመቁት ፈውስን እየሰጠ ይገኛል፡፡
ጌታችን በዛሬው ዕለት ከሞት ለሰወረው ለቅዱስ ነአኵቶ ለአብ "በንግሥና ሳለህ 40 ዓመት ሙሉ የእኔን መከራ አስበው እንባህን ያፈሰስክባት ይህች ምድር እንደ አንተ እስከ ዕለተ ምጽአት እያነባች ትኑር፣ ከቤተ መቅደስህ በእንባ መልክ የሚንጠባጠብ ጠበል ይፍለቅልህ" ባለው አምላካዊ ቃሉ መሠረት የእንባው አምሳያ የሆነው ፈዋሽ ጠበል በዚህ በፎቶው ላይ በሚታየው ማጠራቀሚያ ላይ እንደ እንባ ጠብ ጠብ እያለ ይወርዳል፡፡

የቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!

(በፎቶው ላይ የሚታዩት ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብ ይባርክባቸው የነበሩ መስቀሎች ናቸው።)

ዳግመኛም በዚኽች ዕለት ኅዳር 3 ቀን፡-
+ እነ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባን አስተምረው ያመነኮሱትና ውኃ ይቀዳላቸው የነበረውን አህያቸውን አንበሳ ቢበላባቸው በአህያው ምትክ አንበሳውን 7 ዓመት ለገዳማቸው ውኃ ያስቀዱት የደብረ በንኮሉ ታላቁ አባት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው ዋልድባ ሲደርሱ መነኮሳቱ ‹‹ገዳሙን በአህያ አታስረግጥ›› ቢሏቸው አህዮቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ ያደረጉት አቡነ ፍሬ ካህን ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ሰማያዊ መና ሲመግባቸውና የጌታችንንም ቅዱስ ሥና ደም በሰንበት እያመጣለቸው ያቆርባቸው የነበሩት ሰማዕቱ አቡነ ዓምደ ሚካኤል ዕረፍታቸው ነው፡፡
+ አባ አትናቴዎስና እኅቱ ቅድስት ኢራኢ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
+ ከቆሮንቶስ አገር የተገኙት ቅዱስ አባ ኪርያቆስ ዕረፍታቸው ነው፡፡
ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

11 Nov, 20:26


https://youtu.be/tSzCGbVBx6g

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

08 Nov, 07:54


https://youtu.be/4eIaopj5Wbs

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

07 Nov, 12:09


#ዕረፍቱ_ለአቡነ_ይምዓታ - ጥቅምት 28
አቡነ ይምዓታ ከዘጠኙ ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡

በፎቶው የምታዩት አስደናቂ ፎቶም በትግራይ ውስጥ ከሚገኙት ሺህ ዘመናት ካለፏቸው ጥንታውያን ገዳማት አንዱ የሆነው የአቡነ ይምዓታ ገዳም ነው! እንደሚታወቀው ዘጠኙ ቅዱሳን ሁሉም የነገሥታትና የመኳንንት ልጆች ናቸው፡፡ በራእይም ተገልጦላቸው ወደ ሀገራችንን መጥተው፣ ከሕዝቡ ጋር ዘርና ነገድ፣ ቋንቋና ቀለም ሳይለያቸው በክርስቶስ አንድ ሆነው ለ12 ዓመታትም በፍጹም አንድነት አብረው ከተቀመጡ በኋላ ‹‹እርስ በራሳችን እየተያየን ብንኖር ተድላ ደስታ ይሆንብናልና ተለያይተን እንቀመጥ›› ብለው ተማከረው በተለያየ በዓት አባ ሊቃኖስ በደብረ ቁናጽል፣ አባ ጰንጠሌዎንም በእርሱ ትይዩ በሆነ ቦታ፣ አባ ገሪማ በደብረ መደራ፣ አባ ጽሕማ በደብረ ጸድያ፣ አባ ይምአታ በደብረ ገረዓልታ፣ አባ አፍጼ በደብረ ይሐ፣ አባ አሌፍ በደብረ አኅድአ መኖር ጀመሩ፡፡ አባ አረጋዊ ደግሞ በጣም ርቀው በመሄድ በደብረ ዳሞ በዋሻና በፍርኩታ ውስጥ በተራራም ላይ መኖር ጀመሩ፡፡ አቡነ ይምዓታ ከአክሱም ተነስተው በየመንገዱ ወንጌልን እየሰበኩና ከእመቤታችን ፍቅር የተነሳ "ቅዳሴ ማርያም" እየጸለዩ ሲሄፉ "አብ ጎሕ ወልድ ጎሕ መንፈስ ቅዱስ ጎሕ" እያሉ ሳሉ፤ አሁን ገዳማቸው ከሚገኝበት "ጎሕ" የሚባልበት ቦታ ላይ ደረሱና "ይኩን ስምኪ መካነ ጎሕ" ብለው ሰየሟት! በትሕርምትና በብሕትውናም በገዳማቸው ኖረው ጥቅምት 28 ዕረፍታቸው ሆኗል! የሥጋቸው ሥርዓተ ግንዘት በመላእክት እጅ የተከናወነላቸው ሲሆን እጅግ አስደናቂው ቤተ መቅደሳቸው ሰማይን እንደ ምሰሶ ደግፈው የያዙ የሚመስሉ በጣም ረጃጅም ተራሮች መካከል በአንደኛው ጭፍ ላይ ከባሕር ወለል በላይ በ2300 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ነው፡፡
***
የአቡነ ይምዓታ እጅግ አስገራሚው ቤተ መቅደሳቸው ትግራይ ገርዓልታ ልዩ ስሙ ‹‹ጎሕ›› ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ይገኛል፡፡ ቤተ መቅደሱ ሰማይን እንደ ምሰሶ ደግፈው የያዙ የሚመስሉ በጣም ረጃጅም ተራሮች መካከል በአንደኛው ጭፍ ላይ ይገኛል፡፡ ቤተ መቅደሱ ከባሕር ወለል በላይ በ2300 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ቤተ መቅደሱ ያለበት የተራራው ርዝመት ብቻውን 300 ሜትር ነው፡፡ ቤተ መቅደሱ በር ላይ ለመድረስ በጭንቅና በፍርሃት ሆኖ ተራራውን እንደዝንጀሮ በእጅ እየቧጠጡ መውጣት ይጠይቃል፡፡ የአካባቢው ካህናት ደግሞ እግራችሁን እየደገፉና መረገጫ ቦታው ላይ እያሳረፉ ካልሆነ በቀር ለመውጣት የሚከብድ ተአምራዊ ገዳም ነእ፡፡ ለእጅና ለእግር ማሳረፊያ ትንንሽ ቀዳዳዎችን ብቻ በመጠቀም ነው ቤተ መቅደሱ በር ላይ ለመድረስ የሚቻለው፡፡ በታላቅ ጭንቅና በፍርሃት ሆነው በአካባቢው ካህናት እየታገዙ እንደምንም ብለው ጫፍ ላይ ከደረሱ በኋላ ቁልቁል መመልከት ከአባ ይምዓታ ጋር የነበረ ጌታ አሁንም እየረዳን እንዳለ ይረዱበታል!
***
ቤተ መቅደሱ እጅግ የሚደንቀው በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ ብቻ አይደለም! ውስጡ ያሉት የግድግዳ ላይ ሥዕሎችም በ15ኛው መ/ክ/ዘመን የተሣሉ እጅግ ድንቅና ጥንታዊ ናቸው፡፡ ስለዚሁ የአቡነ ይምዓታ እጅግ አስደናቂ ቤተ መቅደስ ገድለ አቡነ አረጋዊ ‹‹በሞት በዐረፉ ጊዜ የሥጋቸው ሥርዓተ ግንዘት በመላእክት እጅ ነው የተከናወነው፡፡ ይልቁንም ቁመቱና ርዝመቱ ከታላላቅ ገደል እጅግ በጣም የሚበልጥ የድንጋይ ዓምድ ከወንዝ ማዶ ዘንበል ብሎ መጥቶ ሥጋቸውን በክብር ተቀብሎ በተራራው ጫፍ ላይ እስከዛሬም ድረስ ፈጽሞ ሳይነቃነቅና ሳይናወፅ ቀጥ ብሎ ቆሞ ይገኛል›› በማለት ይገልጸዋል፡፡

የአቡነ ይምዓታና የ9ቱ ቅዱሳን ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

07 Nov, 12:09


#ዕረፍቱ_ለአቡነ_ይምዓታ - ጥቅምት 28
አቡነ ይምዓታ ከዘጠኙ ቅዱሳን ውስጥ አንዱ ናቸው፡፡

፡፡

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

06 Nov, 07:56


˙ ✥ ••---• ✞ •---•• ✥

#ዘበእንቲአሃ_ለቤተክርስቲያን_ተጸፋእከ በውስተ ዐውድ ከመ ትቀድሳ በደምከ ክቡር። ዘበእንቲአሃ ዝግሐታተ መዋቅሕት ፆረ ወተዐገሰ ምራቀ ርኩሰ እንዘ አልቦ ዘአበሰ #አምላክ_ዲበ_ዕፀ_መስቀል_ተሰቅለ።

❮ትርጉም❯
#ለቤተክርስቲያን_ብለህ
ልትቀድሳት በደምህ
በአደባባይ በጥፊ ተመታህ።

ንጹሕ ክርስቶስ በአዳም ጥፋት ልትወቀስ
በከንቱ ልትከሰስ አመላለሱህ ከጲላጦስ
ወደ ሄሮድስ
ሁሉን ቻይ ሳለህ ምንም ማድረግ ሳይሳንህ
በአይሁድ እጅ ተገረፍህ!

ወዮ! ወሰን ለሌላት ትዕግስት ስለኛ ብለህ
መከራ ተቀበልህ
ምንም በደል ሳይኖርብህ አምላክ በእንጨት መስቀል ላይ ሰቀሉህ።

#ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

06 Nov, 07:56


ድርሳነ መድኃኔዓለም ዘረቡዕ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

04 Nov, 08:50


ጽጌ እና ፍያታዊ ዘይማን (ጥጦስ)እናስባቸው።
በጌታችን ቀኝና ግራ የተሰቀሉት ሁለቱ ወንበዴዎች
🌼🌼🌼✝️✝️✝️🌼🌼🌼
🌼 ሁለቱ ወንበዴዎች ጥጦስ በቀኙ የተሰቀለው ( ፍያታዊ ዘየማን ) እና ዳክርስ በግራው የተሰቀለው ( ፍያታዊ ዘፀጋ ) :- መተዳደሪያቸው ቅሚያ ነበር። ጌታችን እመቤታችን ዮሴፍ እና ሰሎሜ ከገሊላ በወጡ ጊዜ ወንበዴዎቹ ተከትለዋቸው በበረሃ ቢፈልጓቸውም አስከ ስድስት ቀን አላገኙዋቸውም ነበር። በሰባተኛው ቀን አገኙዋቸውና ዛሬ እግዚአብሔር ከእጃችን ጣላችሁ ብለው እየሮጡ ሄዱባቸው። ሰሎሜ አስቀድማ ልብሷን ጥላላቸው ሸሸች።

🌼ወንበዴዎቹ ከእነዮሴፍ እጅ የተገኘውን ቀምተው ከሄዱ በኃላ ጥጦስ (በቀኙ የተሰቀለው ) ዳክርስን እንዲህ አለው ይቺ ሴት ( እመቤታችንን ማለት ነው ) የነገሥታት ወገን ትመስለኛለች ሕፃኑም ከነቢያት አንዱ ይመስለኛል የቀማናቸውን እንመልስላቸው? ዳክርስም ( በግራ የተሰቀለው ) ጥጦስን (በቀኝ የተሰቀለውን) እንዲህ ያለውን ረኀራሄ ከየት አገኘኸው? ይህን ውንብድና ያስተማርከኝ አንተ ነህ ሌላው ደግሞ ዛሬ የቀማነው የእኔ ድርሻ ነው የራስህን ድርሻ ወስደህ የእኔን ድርሻ እንመልስላቸው ትላለህ? አለው።

🌼እነዚህ ሁለት ቀማኞች አንድ ቀን የቀሙትን አንደኛው ሲወስድ በሌላ ቀን የቀሙትን ደግሞ ሁለተኛው ይወስድ ነበር። በዚህ ዕለት የቀሙት የዳክረስ ( በግራው የተሰቀለው ) ድርሻ ነበር። ጥጦስም ከገሊላ እስከዚህ የቀማነውን አንተ ውሰድ ይህን ለእኔ ስጠኝና ልመልስላቸው አለው። ዳክርስም በዚህ ሐሳብ ተስማማ ዳክርስ ህፃኑ በዝናብ አብቅሎ በፀሐይ አብሰሎ ፍጥረትን የሚመግብ የሁሉ ፈጣሪ መሆኑን ባለመረዳቱ ዕድሉን አልተጠቀመበትም በትንሽ ርኀራኄ ብዙ በረከት አመለጠው ወደ እርሱ ያንዣበበውን ፀጋ ለጓደኛው ሰጠው።

🌼እመቤታችን ሁለቱ ወንበዴዎች ቁመው በዚህ ሐሳብ ሲወያዩ አይታ ፈራች። ወንበዴ የቀማውን ይዞ ይሄዳል እንጂ ለምን ቁሞ ይማከራሉ? ምን አልባት ልጆቻቸው ሄሮድስ የገደለባቸው ሰወች ይሆናሉ በዚህ ሕፃን ምክንያት ልጆቻችን ሞቱብን ብለው ልጄን ሊገሉብኝ ይሆናል ብላ ጽኑዕ ለቅሶን አለቀሰች። ሕፃኑ ኢየሱስ ክርስቶስም እናቱን ድንግል ማርያምን እንዲህ አላት:- አይዞሽ እናቴ አታልቅሺ አይገሉኝም እንመልስላቸው እያሉ ነው። እኔ በቀራኒዮ ስሰቀል እነሱም በቀኜ እና በግራዬ ይሰቀላሉ አንዱ አምላክነቴን አምኖ ይድናል ሁለተኛው ግን አይድንም።

🌼ከዚህ በኃላ ጥጦስ የተባለው ወንበዴ ገንዘባቸውን መለሰላቸውና ጥጦስም ጌታን አቅፎ ይዞ ሲሄድ ሰይፉ ወድቆ ተሰበረበት። በጣም አዘነ። ጌታ የሰይፍህን ስብርባሪ ሰብስብ አለው። ጥጦስ የሰይፉን ስብርባሪ ሰበሰበ። ጌታም እንደቀድሞው ይሁንልህ አለው።ሰይፉም እንዳልተሰበረ ሆነ። ጥጦስ ሕፃኑ ከነቢያት ወገን ይመስለኛል ብሎ የገመተው ግምት እውን ሆነለት ። ተአምራቱን አየና አደነቀ።

🌼ጌታ ጥጦስን እንዲህ አለው:- አዳምን ቀድመኸው ገነት ትገባለህ። ጥጦስም ሄዶ ጌታ የነገረውን ሁሉ እና ያደረገለትን ተአምራት ለጓደኛው ነገረው። ጓደኛው ግን አላመነም። ጥጦስ የተባለው ወንበዴም ጌታ በተሰቀለ ጊዜ በጌታ ቀኝ ተሰቅሎ ፀሐይ ስትጨልም አይቶ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት አምኖ " ጌታ ሆይ በመንግሥትህ በመጣህ ጊዜ አስበኝ " አለው። ኢየሱስም እውነት እልሃለሁ ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ አለው። የሉቃስ ወንጌል 23:42 ጌታ አዳምን ቀድመኸው ገነት ትገባለህ ብሎ በጫካ የሰጠውን ተስፋ በመስቀል ላይ ፈጸመለት። ምነው ጌታችንን በወንበዴዎች መካከል ሰቀሉት ጌታስ ስለምን ተሰቀለ ቢሉ አይሁድ ጠልተውታልና ኢየሱስ ናዝራዊ ንጉሥ እንጂ ነህ ግራ ቀኝ ቢትወደድ ይገባሃል እያሉ ሲሣለቁበት ነው። ጌታችን ግን ኃላ በዕለተ ምፅአት ጊዜ ጻድቃንን በቀኝ ኃጥአንን በግራ አቁሜ የማጸድቅ የምኮንን እኔ ነኝ ሲል ነው።

🌼ጌታም እራሱን ወደ ጥጦስ ዘንበል አድርጎ ምድረ ግብፅ ስንወርድ የነገርኩህ ሁሉ ደረሰ ከሞት በቀር ሌላ ነገር የቀረኝ የለም ሂድ ገነት ግባ ብሎ ደመ ማኀተሙን ሰጥቶ ሰደደው የገነት ጠባቂዋ ሱራፊ መልአክ ደመ ማኀተሙን ፈርቶ እየሸሸ አንተ ማነህ የት ትገባለህ ቢለው ወንድሜ አልሰማህም አምላክ እንጂ ወርዶ ተወልዶ ዓለምን ሁሉ አዳነው አለው አንተስ ማነህ አዳምን ነህ አብርሃምን ይስሐቅን ነህ ያዕቆብን ነህ እያለ ደጋጎቹን እየጠራ ቢጠይቀው ሁሉንም አይደለሁም እጄን በሰው ደም ነክሬ የምኖር ወንበዴ ነበርሁ አለው።

🌼ለእንደዚህ አይነት ያለ ክብር ያበቃህ ምንድነው ቢለው 7ቱ ተአምራት ሲሰሩ አይቼ አምላክነቱን ተረድቼ ብለምነው ለእንደዚህ ያለ ክብር ጸጋ አበቃኝ ብሎ ለ 5500 ዘመን ተዘግታ የነበረችቱን ገነት በጌታችን ደመ ማኀተም ከፍቶ አዳምን ቀድሞ ገነት ገባ።
ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንገተኛ ሞት ሰውሮ በመጨረሻዋ ደቂቃችንም ቢሆን እንደ ጥጦስ (ፍያታዊ ዘየማን ) በቸርነቱ አስቦ መንግሥተ እርስቱን ያውርሰን አሜን።

ምንጭ: የእመቤታችን ጉዞ ከገሊላ ወደ ግብፅ እና ኢትዮጵያ እንዲሁም መዝገበ ጸሎት።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

04 Nov, 08:50


ጽጌ እና ፍያታዊ ዘይማን (ጥጦስ)እናስባቸው።
በጌታችን ቀኝና ግራ የተሰቀሉት ሁለቱ ወንበዴዎች
🌼🌼🌼✝️✝️✝️🌼🌼🌼

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

04 Nov, 07:57


በዕረፍትህ መታሰቢያ ቀን ‹‹የአባ አቢብ ፈጣሪ ሆይ! ኃጢአቴን ሁሉ ተውልኝ› ብሎ አንዲት ጸሎትን የጸለየውን ሁሉ እኔ ኃጢአቱን እተውለታለሁ››
‹‹በቅዱሱ ቃል ኪዳን እንጠቀምበት!››
ከአቡነ አቢብ በዓለ ዕረፍት ረድኤት በረከት ይክፈለን!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

31 Oct, 16:02


ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
ፍርድ አዘል መግለጫ
21/02/2017 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

31 Oct, 08:28


''የዓለም ብርሃን ፀሐይ ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስን የወለድሽልን እውነተኛውን ብርሃን ለዓለም የሰጠን ብርሃን ዘበአማን ዘያበርህ ለኩሉ ሰብእ(ለሰው ልጆች ሁሉ በእውነት ብርሃንን ያበራ ) ተብሎ የተወደሰን ንጉስ ክርስቶስን ያስገኘሽልን አማናዊቷ ምስራቅ የፀሀይ መውጫ ሰላማዊት እመቤት ወላዲተ ብርሃን
ድንግል ማርያም ሆይ አንቺ ሰላማዊት እመቤት ሆይ የኃጢአት ጨለማ ውጦኛል ደክሜአለሁ ህይወቴ ያላንቺና ያለ ልጅሽ ብርቱ ጨለማ ናትና ወደ ልቤ ተመለሺ...''

(ዮሐ8፡12፤ ዮሐ 9፡6፤ ውዳሴ ማርያም ዘሰኑይ )

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 16:25


ልዩ ማሳሰቢያ ከራዕይ ዮሐንስ 20
20/02/2017 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


ኢየሱስ ክርስቶስ ካህኑ ለዓለም ንጉሠ ፅዮን ወንጉሠ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ
ድንግል ማርያም እሙ ወእምነ ንግሥተ ፅዮን ወንግሥተ ነገሥታት ዘኢትዮጵያ

🥢 ዓለሙን ስለ ክፋታቸው ክፉዎቹንም ስለ በደላቸው እቀጣለሁ የትዕቢተኛዎችንም ኵራት አዋርዳለሁ።
ትንቢተ ኢሳያስ 13፡11

በ 19/2/2017 ድንቃ ድንቅ አስተማሪ ምስክርነት ይለቀቃል 👇👇👇

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


የእህታችን እህተ ማርያም እጹብ ድንቅ ምስክርነት
ከዱባይ
19/2/2017

👉 እውነትን  ጨብጣችሁ  እግዚአብሔርን  ጠይቃችሁ  መልስም  አግኝታችሁ  የተረጋገጠ  ተስፋን  ጨብጣችሁ ያላችሁ  የእግዚአብሔር  ቤተሰቦች  ባለድል  ናችሁ።  እውር  ዓይናማውን  ቢተቸው  እኔ  ልምራህ  ቢለው  ምንኛ ፌዝ  እንደሚሆን  ትረዳላችሁ።  ስለዚህ  ማንም  ተነስቶ  በሚደረድረው  ከንቱ  ቃል  ልባችሁን  አታስቱ!  በቅርቡ ሁሉንም  እንደቃሉ  ሲፈጸም  ታያላችሁ።  ለመሆኑ  በኢትዮጵያ  የዓለም  ብርሃን  የተገለጹ  የልዑል  የፍርድ ቃሎች  መልእክቶች  ሲፈጸሙ  አላያችሁም?  የቀሩትስ  ለመፈጸማቸው  ምልክታቸውን  እየሰጡ  የሰውን  ልጅ በእግዚአብሔር  የፍርድ  ሚዛን  ተለክተው  ሲካተቱ  እንደምታዩት  አልተረዳችሁምን?  የጥርጥር  ችግር  ካለባችሁ ልዑልን  ጠይቁ  ከሰው  ይልቅ  ከሱ  የሚሰጣችሁ  ማረጋገጫ  ይበልጣልና  መጠየቅ  መብታችሁ  ስለሆነ  ጠይቁ ተረዱ  ተዘጋጁ  በቃ!  ስላበቃ  ሁሉም  የምታዩት  የሚያስቷችሁ  የአውሬው  የዘንዶው  የሐሰተኛው  ነቢይ  ደቀ መዝሙሮች ቅጥረኞች ሆድ አደሮች በሙሉ በቅርብ በክፉ መከራና ስቃይ ሲወገዱ ታዩአቸዋላችሁ።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ ዘጠነኛ መልእክት ተጻፈ ታህሳስ 21 ቀን 2013 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


የእህታችን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ
19/2/2017

👉 ከፈጣሪዬም የተማርኩት ትምክህትን አርቆ ትሕትናን መልበስን መልካም ስለሆነ ነው እንጂ ሊነገርም ሊታሰብ የማይችል ስጦታውን ጌታ ለእኔ ለትንሹ ባርያው ሰጥቷአል። ትምክህት ከጨለማ ስለሆነ በመመካት አልናገርም መግለጽ ግድ ካልሆነብኝ በቀር። የሰው ዘር አድምጥ መሪዎችህ ገዥዎችህ በከፍታ ላይ አቁመህ የምታያቸው የምትንቀጠቀጥላቸው ጣዖቶችህ ክቡር እከሌ፣ አዋቂው፣ ባለሙያው፣ ሊቃውንቱ፣ የጦር ባለሙያው፣ ኢኮኖሚስቱ፣ ባለሃብቱ፣ ቢሊኒየሩ፣ ኢንደስትርያሊስቱ፣ የህክምና ጠበብቱ፣ መሃንዲሱ፣ የአየር ንብረት አዋቂው፣ የጦር አለቃው፣ ተመራማሪው፣ የፖለቲካ ሳይንቲስቱ፣ ኧረ ምኑ ተቆጥሮ የሊቁ፣ የአዋቂው፣ የአባይ ጠንቋዩ፣ የጦር ኤክስፐርቱ ወዘተ እኚህ ሁሉ ምን ፈየዱ? ምንስ ለወጡ? ምንስ አመጡልህ? በየአገሩ ሕዝባቸውን በመግዛት፣ በማስጨነቅ፣ ወደ ጥፋት በመንዳት ላይ ያሉ ከመንደር እስከ አገር፣ ክፍለ አሕጉር የተኮለኮሉ ገዥዎች መቼ ጊዜ ለፈጣሪ ትእዛዝ ጆሮ ሲሰጡ ታየ? የእነሱ ጥፋት ምድርን ሸፍኖ ሰማይን አዳርሷል። የዘመኑን ፊደል ቆጠሩ ሁሉን አዋቂ ሆኑ። ሰርቆ፣ ነጥቆ፣ ገሎ፣ አመንዝሮ፣ ዋሽቶ፣ አታሎ በየትኛውም ቀን ተሰማርቶ ገንዘብን ሰብስቦ ሕዝብን አስጨንቆ መኖሩ ሕልማቸውና ደስታቸው ከሆነ ዘመናት አለፈም ተቆጠረም።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ሦስት ገጽ 5 የተወሰደ ተጻፈ መጋቢት 19 2001 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


የወንድማችን ወልደ ተክለሃይማኖት እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = መተሐራ
19/2/2017

👉 ዛሬ በአገራችን ያለው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ እንደሆነ እንኳን በልዑል የሚታመነው ቀርቶ የጠፋውም 
ትውልድ ግራ ገብቶት እንደ ውኃ ላይ ኩበት ሲዋልል እየታየ ነው። አገራችን ልትፈርስ ነው በዘር ልትገነጣጠል 
ነው እርስ በእርስ ልንጫረስ ነው እየተባለ ሁሉም በድንጋጤ የተዋጠበት ዘመን ነው። ሁሉም እንደሚያውቀው 
አገራችን ኢትዮጵያን ወደዚህ ደረጃ ያደረሳት ዛሬ ጥግ ይዤአለሁ የሚለው ሁሉም የሚጠራው ወያኔ በሚለው 
ስሙ እኔም የማውቀው ዘረኛ ቡድን ነው። 27 ዓመት ሙሉ ሲፈጭህ ሲቆላህ የቆየው ክፉ ወፍጮ ከአጠገብህ 
ሳይርቅ በሩቅ መቆጣጠሪያ እየተቆጣጠረህ ግራ ተጋብተህ እንደ አሻሮ ትቆላለህ፤ መፍትሄ የለውም። እሱን 
ተክቶ የመጣው ከራሱ ማኅፀን የወጣው መንግሥት ደግሞ ችግርህን ከድጡ ወደማጡ አድርጎብሃል።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ስምንት ገጽ 31 የተወሰደ ተጻፈ ተጻፈ ታህሳስ 21 2011

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


የእህታችን ዓመተ ጊዮርጊስ እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ
19/2/2017

👉  ያለወላዲተ አምላክ አማላጅነት ዓለም አይድንም
👉 ያለወላዲተ አምላክ አማላጅነት ሀገር አይድንም
👉 ያለወላዲተ አምላክ አማላጅነት ቤተሰብ አይድንም ።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


የወንድማችን ወልደ አማኑኤል እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህርዳር
19/2/2017
ክፍል ፪

👉 ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫ እና መመስገኛ ምድር
👉 ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
👉 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
👉 ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዥ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


የወንድማችን ወልደ አማኑኤል እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህርዳር
19/2/2017
ክፍል ፩

👉 ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫ እና መመስገኛ ምድር
👉 ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
👉 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
👉 ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዥ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

30 Oct, 05:39


የወንድማችን ሰይፈ ሥላሴ እጹብ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = አዲስአበባ
19/2/2017

👉 ኢትዮጵያን የጠላ፥ ድንግልን ተዋሕዶን እምነት የጠላ፥ ባንዲራዋን የጠላ ሁሉ ይጠረጋል እንጂ በፍጹም
አይድንም። ማምለጫም መዳኛም መንገድ ፍጹም የለውም። በሰሜን በምዕራብ በምሥራቅ በደቡብ የመሸጋችሁ
አገራችንን እንደ አንጋሬ ቆዳ ወጥራችሁ ያስጨነቃችኋት ሁሉ በከፋ እሳት ትጠረጋላችሁ እንጂ ከእንግዲህ
ዕድሜ የላችሁም፤ የሚጠቅማችሁን ጊዜ በደል በበደል ላይ፣ አመጽ በአመጽ ላይ እየጨመራችሁ መጣችሁ
እንጂ ቅንጣት የመጸጸት ምልክት አልታየባችሁም። በመሆኑም ስታፌዙ ጊዜው አለቀ ተከደነ። የመጣውን
መቀበል ብቻ ነው።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ስምንት ገጽ 32 የተወሰደ ተጻፈ 21/4 /2011

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Oct, 23:59


የወንድማችን ወልደ ተክለሃይማኖት እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = መተሐራ
19/2/2017

👉 ዛሬ በአገራችን ያለው ሁኔታ እጅግ አስፈሪ እንደሆነ እንኳን በልዑል የሚታመነው ቀርቶ የጠፋውም 
ትውልድ ግራ ገብቶት እንደ ውኃ ላይ ኩበት ሲዋልል እየታየ ነው። አገራችን ልትፈርስ ነው በዘር ልትገነጣጠል 
ነው እርስ በእርስ ልንጫረስ ነው እየተባለ ሁሉም በድንጋጤ የተዋጠበት ዘመን ነው። ሁሉም እንደሚያውቀው 
አገራችን ኢትዮጵያን ወደዚህ ደረጃ ያደረሳት ዛሬ ጥግ ይዤአለሁ የሚለው ሁሉም የሚጠራው ወያኔ በሚለው 
ስሙ እኔም የማውቀው ዘረኛ ቡድን ነው። 27 ዓመት ሙሉ ሲፈጭህ ሲቆላህ የቆየው ክፉ ወፍጮ ከአጠገብህ 
ሳይርቅ በሩቅ መቆጣጠሪያ እየተቆጣጠረህ ግራ ተጋብተህ እንደ አሻሮ ትቆላለህ፤ መፍትሄ የለውም። እሱን 
ተክቶ የመጣው ከራሱ ማኅፀን የወጣው መንግሥት ደግሞ ችግርህን ከድጡ ወደማጡ አድርጎብሃል።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ስምንት ገጽ 31 የተወሰደ ተጻፈ ተጻፈ ታህሳስ 21 2011

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Oct, 23:59


የእህታችን እህተ ማርያም እጹብ ድንቅ ምስክርነት
ከዱባይ
19/2/2017

👉 እውነትን  ጨብጣችሁ  እግዚአብሔርን  ጠይቃችሁ  መልስም  አግኝታችሁ  የተረጋገጠ  ተስፋን  ጨብጣችሁ ያላችሁ  የእግዚአብሔር  ቤተሰቦች  ባለድል  ናችሁ።  እውር  ዓይናማውን  ቢተቸው  እኔ  ልምራህ  ቢለው  ምንኛ ፌዝ  እንደሚሆን  ትረዳላችሁ።  ስለዚህ  ማንም  ተነስቶ  በሚደረድረው  ከንቱ  ቃል  ልባችሁን  አታስቱ!  በቅርቡ ሁሉንም  እንደቃሉ  ሲፈጸም  ታያላችሁ።  ለመሆኑ  በኢትዮጵያ  የዓለም  ብርሃን  የተገለጹ  የልዑል  የፍርድ ቃሎች  መልእክቶች  ሲፈጸሙ  አላያችሁም?  የቀሩትስ  ለመፈጸማቸው  ምልክታቸውን  እየሰጡ  የሰውን  ልጅ በእግዚአብሔር  የፍርድ  ሚዛን  ተለክተው  ሲካተቱ  እንደምታዩት  አልተረዳችሁምን?  የጥርጥር  ችግር  ካለባችሁ ልዑልን  ጠይቁ  ከሰው  ይልቅ  ከሱ  የሚሰጣችሁ  ማረጋገጫ  ይበልጣልና  መጠየቅ  መብታችሁ  ስለሆነ  ጠይቁ ተረዱ  ተዘጋጁ  በቃ!  ስላበቃ  ሁሉም  የምታዩት  የሚያስቷችሁ  የአውሬው  የዘንዶው  የሐሰተኛው  ነቢይ  ደቀ መዝሙሮች ቅጥረኞች ሆድ አደሮች በሙሉ በቅርብ በክፉ መከራና ስቃይ ሲወገዱ ታዩአቸዋላችሁ።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃናዊ መንግሥት የወጣ ዘጠነኛ መልእክት ተጻፈ ታህሳስ 21 ቀን 2013 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Oct, 23:59


የእህታችን እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ
19/2/2017

👉 ከፈጣሪዬም የተማርኩት ትምክህትን አርቆ ትሕትናን መልበስን መልካም ስለሆነ ነው እንጂ ሊነገርም ሊታሰብ የማይችል ስጦታውን ጌታ ለእኔ ለትንሹ ባርያው ሰጥቷአል። ትምክህት ከጨለማ ስለሆነ በመመካት አልናገርም መግለጽ ግድ ካልሆነብኝ በቀር። የሰው ዘር አድምጥ መሪዎችህ ገዥዎችህ በከፍታ ላይ አቁመህ የምታያቸው የምትንቀጠቀጥላቸው ጣዖቶችህ ክቡር እከሌ፣ አዋቂው፣ ባለሙያው፣ ሊቃውንቱ፣ የጦር ባለሙያው፣ ኢኮኖሚስቱ፣ ባለሃብቱ፣ ቢሊኒየሩ፣ ኢንደስትርያሊስቱ፣ የህክምና ጠበብቱ፣ መሃንዲሱ፣ የአየር ንብረት አዋቂው፣ የጦር አለቃው፣ ተመራማሪው፣ የፖለቲካ ሳይንቲስቱ፣ ኧረ ምኑ ተቆጥሮ የሊቁ፣ የአዋቂው፣ የአባይ ጠንቋዩ፣ የጦር ኤክስፐርቱ ወዘተ እኚህ ሁሉ ምን ፈየዱ? ምንስ ለወጡ? ምንስ አመጡልህ? በየአገሩ ሕዝባቸውን በመግዛት፣ በማስጨነቅ፣ ወደ ጥፋት በመንዳት ላይ ያሉ ከመንደር እስከ አገር፣ ክፍለ አሕጉር የተኮለኮሉ ገዥዎች መቼ ጊዜ ለፈጣሪ ትእዛዝ ጆሮ ሲሰጡ ታየ? የእነሱ ጥፋት ምድርን ሸፍኖ ሰማይን አዳርሷል። የዘመኑን ፊደል ቆጠሩ ሁሉን አዋቂ ሆኑ። ሰርቆ፣ ነጥቆ፣ ገሎ፣ አመንዝሮ፣ ዋሽቶ፣ አታሎ በየትኛውም ቀን ተሰማርቶ ገንዘብን ሰብስቦ ሕዝብን አስጨንቆ መኖሩ ሕልማቸውና ደስታቸው ከሆነ ዘመናት አለፈም ተቆጠረም።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ሦስት ገጽ 5 የተወሰደ ተጻፈ መጋቢት 19 2001 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Oct, 23:59


የወንድማችን ወልደ አማኑኤል እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህርዳር
19/2/2017
ክፍል ፪

👉 ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫ እና መመስገኛ ምድር
👉 ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
👉 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
👉 ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዥ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Oct, 23:59


የወንድማችን ወልደ አማኑኤል እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህርዳር
19/2/2017
ክፍል ፩

👉 ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫ እና መመስገኛ ምድር
👉 ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም
👉 ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን
👉 ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዥ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Oct, 23:59


የእህታችን ዓመተ ጊዮርጊስ እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ
19/2/2017

👉  ያለወላዲተ አምላክ አማላጅነት ዓለም አይድንም
👉 ያለወላዲተ አምላክ አማላጅነት ሀገር አይድንም
👉 ያለወላዲተ አምላክ አማላጅነት ቤተሰብ አይድንም ።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

29 Oct, 23:59


የወንድማችን ሰይፈ ሥላሴ እጹብ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = አዲስአበባ
19/2/2017

👉 ኢትዮጵያን የጠላ፥ ድንግልን ተዋሕዶን እምነት የጠላ፥ ባንዲራዋን የጠላ ሁሉ ይጠረጋል እንጂ በፍጹም
አይድንም። ማምለጫም መዳኛም መንገድ ፍጹም የለውም። በሰሜን በምዕራብ በምሥራቅ በደቡብ የመሸጋችሁ
አገራችንን እንደ አንጋሬ ቆዳ ወጥራችሁ ያስጨነቃችኋት ሁሉ በከፋ እሳት ትጠረጋላችሁ እንጂ ከእንግዲህ
ዕድሜ የላችሁም፤ የሚጠቅማችሁን ጊዜ በደል በበደል ላይ፣ አመጽ በአመጽ ላይ እየጨመራችሁ መጣችሁ
እንጂ ቅንጣት የመጸጸት ምልክት አልታየባችሁም። በመሆኑም ስታፌዙ ጊዜው አለቀ ተከደነ። የመጣውን
መቀበል ብቻ ነው።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ስምንት ገጽ 32 የተወሰደ ተጻፈ 21/4 /2011

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

26 Oct, 17:04


https://youtu.be/bVtkFwy2aJw

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

24 Oct, 07:21


እንኳን አደረሳችሁ! #ጥቅምት_14 ቤተክርስቲያን የ 3 ታላላቅ አባቶችን መታሰቢያ ታከብራለች:-

#አንደኛው_አቡነ_አረጋዊ ( ዘሚካኤል ) የአባቱ ስም ይሰሃቅ ሲሆን የእናቱ
ስም እድና ይባላል፡፡ አባቱ ከሮም ነገሥታት ወገን ነው፡፡
ቤተሰቦቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ታማኝ የእግዚአብሔር ሰዎች
ነበሩ፡፡ ልጅ ግን አልነበራቸውምና ልጅ እንዲሰጣቸው
ቤተክርስቲያን በመሄድ ይጠይቁት ነበር፡፡ እግዚአብሔር
ልመናቸውን ሰምቶ ወንድ ልጅ ሰጣቸው ስሙንም ገብረ አምላክ
አሉት እድሜው ለትምህርት ሲደርስ መንፈሳዊ ትምህርትን ተማረ
ዕለት ዕለት ቤተክርስቲያን በመሄድ በጸሎት ይተጋ ነበር፡፡
ወላጆቹም ከነገሥታት ወገን ሚስት አጩለት እርሱ ግን እምቢ
ብሎ ፅርዕ (ግሪክ) አገር ደውናሶ ወደምትባል አባ ጳኩሚስ
ወደሚኖርበት ገዳም በመሄድ ምንኩስናን መቀበል እንደሚፈልግ
ነገራቸው አባ ጳኩሚስ የንጉሥ ልጅ ሆነህ መመንኮስ ይቻልሃልን
ቢለው «አባቴ የምድር መንግሥት ኃላፊ ነው ነገር ግን
የማያልፈው የማይጠፈውን ዘለዓለማዊ መንግሥት እወርስ ዘንድ
እፈልጋለሁ» ቢለው ለምንኩስና የሚያስፈልገውን ሥርዓተ
ትምህርት ተምሮ በ14 አመቱ መነኮሰ፡፡
ወደ ኢትዮጵያም ከመጡ በኋላ የደብረ ዳሞን ተራራ ስለወደዱት
«ከዚህ ተራራ ላይ ወጥቼ ስለ ኃጢአቴ እናዘዝና ስለ በደሌ
ይቅርታ እጠይቅ ዘንድ ፍቀድልኝ በማለት እግዚአብሔርን በጸሎት
ጠይቀው ሁለት ሱባኤ (14 ቀን) በዚያው ተቀመጡ ከዚያም ወደ
ተራራ ያውጣህ ዘንድ ታላቅ ዘንዶ ይላክልሃል ተባሉ ቁመቱ ስልሳ
ክንድ የሆነ ታላቅ ዘንዶ ተልኮላቸው ወደ ተራራ ወጡ በዚያም
በደስታ እግዚአብሔርን አመሰገኑ ዳቦ አንስተው ባርከው
ተመገቡ የቦታውን በረከት አዩ ከዚያ ቀን ወዲያ ምንም
አልቀመሱም ነበር ጌታችን ተገልፆ ቃል ኪዳን ገባላቸው
መታሰቢያ ያደረገ ዝክር የዘከረ መባ ያገባ ; በመንግስቴም
አከብረዋለሁ፤ የሞት ጥላ አያርፍብህም እንደ ነቢያት
ትሰወራለህ አላቸው በ99 ዓመታቸው ጥር 14 በዚሁ ገዳም
ተሰወሩ ፡፡

#ሁለተኛው_ቅዱስ_ገብረ_ክርስቶስ የአባቱ ስም ንጉሥ ቴዎድስዮ እናቱ ንግሥት መርኬሃ ይባላሉ፡፡ ልጅ ስላልነበራቸው ዘወትር ያዝኑ ነገር፡፡ በጎልጎታ ተንበርክከው ልጅ እንዲሰጠቸው ይጸልዩና ይሳሉ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ልመናቸውን ሰምቶ ልጅ ሰጣቸው ፡፡ ልጁንም አብደል መሲህ አሉት ትርጓሜው ገብረ ክርስቶስ ማለት ነው፡፡ መንፈሳዊውን
ሥጋዊውን ትምህርት እየተማረ አደገ ወላጆቹም የልጃቸውን ደስታ ለማየት ከሮም ነገሥታት ወገን ሚስት አጩለት በሥርዓተ ቤተክርስቲያን የቁስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ አባ ቴውፍሎስ
ሥርዓተ ጸሎት ተደርጎ ጋብቻቸው ተፈፀመ ፡፡ ወደ ጫጉላ ቤትም ገቡ በመንፈቀ ሌሊትም ተነስተው ጸሎት እንዲያደርጉ ጠየቃት፡፡ ጸሎት ካደረጉ በኋላ የሙሽርነት ልብሱን አውልቆ ተርታ ልብስ ለበሰ እግዚአብሔር ካንቺ ይሁን ከዲያቢሎስ ተንኮል ያድንሽ
ብሏት ሄደ፡፡ ከሰንበት በቀር ምንም ሳይቀምስ በጾም በጸሎት 15 ዓመት በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ደጃፍ ተቀመጠ፡፡

እንግዲህ ከአባቴ ማዕድ ፍርፋሪ እንጂ ሌላ ምፅዋትን አልሻም በማለት ከንጉሱ አባቱ ዘንድ ቀርቦ ከመአድህ የተረፈውን ፍርፋሪ እየበላሁ በቤት አኑረኝ ብሎ ለመነው፡፡ አባቱም የእኔም ልጅ በሰው ሀገር እንዲህ ይንከራተታል በማለት ቤት አስርቶ አስቀመጠው አገልጋዮቹ በዚህ ቀንተው ይመቱት ፂሙን ይነጩት ምራቅ ይተፉበት ሽንታቸውን ሸንተው ይደፉበት ነበር ፡፡ የቆሰለ ሰውነቱን ውሾች ይልሱትም ነበር እርሱ ግን ይህንን ሁሉ መከራ ተቀብሎ ለ15 ዓመት ኖረ፡፡ ይህንን ስለ ክርስቶስ ታገሰ በመጨረሻም ወረቀትን አስመጥቶ ለወላጆቹ የነሱ ልጅ መሆኑን ገልፆ ጥቅምት 14 ቀን ዐረፈ፡፡ በዕረፍቱም ቀን ብዙ ድውያን ዕውራን አንካሶች ሬሳውን በመዳሰስ ተፈወሱ ፡፡ የጻድቆቹ በረከት ይደርብን.

#ሦስተኛው በዛሬዋ ቀን የኢትዮጰያዊቷ ንግስት ህንደኬ በጀሮንዷ የሆነውን ጀንደረባውን ያጠመቀው ታሪኩ በሐዋርያት ስራ ምዕራፍ 8፤27 ላይ ተገልጾ የሚገኘው ሐዋርያው ፊሊጰስ ያረፈበት ቀን ነው:: ቅዱስ ፊልዾስ ሐዋርያ "+
+በዘመነ ሐዋርያት በዚህ ስም የሚጠሩ አባቶች 2 ነበሩ:: አንደኛው ከ12ቱ ሐዋርያት ሲቆጠር ዛሬ የምናከብረው ደግሞ ከ72ቱ አርድእት ይቆጠራል:: ቅዱስ ፊልዾስ ያደገው የኖረውም በቂሣርያ አካባቢ ሲሆን ባለ ትዳር የልጆች አባት ነው::
+ጌታ ሲጠራው እንኩዋ 4 ደናግል ሴቶች ልጆች ነበሩት:: ከጌታ ሕማማት በፊት ተልኮ አስተምሯል:: ከበዓለ ሃምሳ በኋላም 7ቱ ዲያቆናት ሲመረጡ አንዱ እርሱ ነበር:: (ሐዋ. 6) በቅዱስ እስጢፋኖስ መሪነትም 8ሺውን ማሕበር አገልግሏል::
+ቅዱስ እስጢፋኖስ ተገድሎ 8ሺው ማሕበር ሲበተንም ቅዱስ ፊልዾስ 4ቱን ልጆቹን አስከትሎ ወደ ሰማርያ ወርዷል:: በዚያም መሠሪ ስምዖንን ጨምሮ የሃገሪቱን ሰዎች አሳምኖ አጥምቁዋል::
+መቼም ቢሆን እኛ ኢትዮዽያውያን የማንዘነጋው ግን ጃንደረባውን ባኮስን ማጥመቁን እና ለሃገራችን የወንጌልን ብርሃን መላኩን ነው:: ጃንደረባው ቅዱስ ባኮስ ከጉዞ መልስ ትንቢተ ኢሳይያስን (ኢሳ. 53) ሲያነብ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ቀርቦ ምሥጢረ ሥጋዌን አስረድቶታል::
+ሠረገላውም ቁሞለት ቅዱስ ባኮስን አጥምቆት ተነጥቆ ሔዷል:: (ሐዋ. 8:26) ቅዱስ ፊልዾስ በቀሪ ዘመኑ ከተባረኩ 4 ደናግል ልጆቹ ጋር ሲሰብክ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል::
የአባቶቻችን በረከታቸው ይደርብን።

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

24 Oct, 07:21


እንኳን አደረሳችሁ! #ጥቅምት_14 ቤተክርስቲያን የ 3 ታላላቅ አባቶችን መታሰቢያ ታከብራለች:-

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

23 Oct, 11:04


https://www.youtube.com/watch?v=ikx1yukxZ6k

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

20 Oct, 10:39


ታላቁ ጻድቅ አባ ዘወንጌል ዘኢትዮጵያ አመታዊ መታሰቢያ ቀን ዛሬ ጥቅምት 10 ነው ።

እንኳን ለታላቁ አባታችን አባ ዘወንጌል ዘኢትዮጵያ 5ኛ አመት የዕረፍታቸው መታሰቢያ ቀን አደረሰን አደረሳችሁ። የአባታች በረከት ረድኤት በሁላችንም ላይ ይደርብን።

ጥቅምት 10/2017 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

19 Oct, 07:15


#በላይ_ዘለቀ_ጊዮርጊስ_ያዉቃል_ይላል! #በቅዱስ_ጊዮርጊስ_በጣም_ያምን_ነበር
...ንጉሱ ደብረማርቆስ የመጡ ጊዜ አስራ ሁለት ሺህ ብር ሰጥተዉት ሄዱ። ከማርቆስ ወደ ቢቸና ሲጉዋዝ አንዱ መጥቶ "ቤቴ ተቃጠለ" ገንዘብ ሲሰጠዉ ሌላዉ መጥቶ "ከብቴ ተዘረፈ" ሲል ገንዘብ ሲሰጠዉ እንዲህ ሲል ገና ቢቸና ሳይገባ 12ሺህ ብሩ አለቀ። "ጊዮርጊስ ያዉቃል" ይላል በላይ ዘለቀ።በቅዱስ ጊዮርጊስ በጣም ያምናል። ፆመ ፍልሰታ ሲሆን ሁል ጊዜ ሱባኤ ይገባል። "እኔ የዘለቀ ልጅ!" ይላል ሲቆጣ። "በምድር በሰማይ የሚያስጉዘዉ! በላይ የወንዶች ቁና" ይላል ሲፎክር። ባንዳነትን አድርባይነትን ሎሌነትን አጥብቆ ይጠላም ነበር...።

የጀግኖች አባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ይመስገን!

https://t.me/Yetewahedoarbegnoch

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

18 Oct, 07:31


‹‹በመቃብሩ ላይ ወድቃችሁ ይቅር በለን በሉት››

አባ ኪሮስ በጌታችን ትእዛዝ ወደ ሳት ገዳም በሄደ ጊዜ በቤተ ክርስቲያኒቱን ሲሳለማት የእመቤታችንን ሥዕል ተመለከተና ከዐይኖቹ ዕንባ እያፈሰሰ ‹‹እመቤቴ ሆይ አስቢኝ›› አላት፡፡ ሥዕሊቱም አፍ አውጥታ በሰው አንደበት ‹‹ኪሮስ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው፣ ከዚህ ግን አልፈህ ወደ ሌላ ቦታ አትሂድ የአባትህን ዐፅም ትጠብቅ ዘንድ ይገባሃል›› አለችው፡፡ እርሱም ይህን ሰምቶ በፊቷ 700 ሰግደትን ሰገደ፡፡

ከዚኽም በኋላ አባ ኪሮስ በዚያ በተናቀ ቦታ ላይ በጽኑ ሕማም የታመመ ሰውን አገኘ፡፡ በታመመውም ሰው ራስጌ ቅዱስ ሚካኤል፣ በግርጌው ቅዱስ ገብርኤል፣ በቀኙ ቅዱስ ሩፋኤል፣ በግራው ቅዱስ ሰዳካኤል ሆነው በክንፋቸው ጋርደው ሲጠብቁት አገኛቸው፡፡ ከሰውም እነርሱም ማንም ያያቸው የለም፡፡ ለአባ ኪሮስም ሰላምታ በሰጡት ጊዜ እርሱም እጅግ አድንቆ ‹‹በልዕልና ነዋሪዎች ሆይ! ከዚህ ለምን ተቀመጣችሁ?›› አላቸው፡፡ እነርሱም ‹‹ይህን ድኃ እንጠብቀው ዘንድ እግዚአብሔር አዞናል›› አሉት፡፡ አባ ኪሮስም ‹‹እስከመቼ ነው የምትጠብቁት?›› ሲላቸው ቅዱሳን መላእክቱም ‹‹እግዚአብሔር እስኪያሳርፈው ድረስ›› አሉት፡፡ አባ ኪሮስም ወደ ድኃው ጠጋ ብሎ ‹‹በዚህ በተናቀ ቦታ ተጥለህ መኖር ከጀመርህ ምን ያህል ጊዜ ሆነህ?›› አለው፡፡ በሕማም የተያዘው ድኃውም ‹‹በዚህ ቦታ 65 ዓመት ኖርኩ›› አለው፡፡ ከዚህም ውስጥ ሃያውን ዓመት በሕማም እንደኖረ ነገረው፡፡ አባ ኪሮስም ‹‹የገዳሙ አበ ምኔትና የገዳሙ መነኮሳት ይጎበኙሃልን?›› አለው፡፡ ድኃው ሚሳኤልም ‹‹አባቴ ሆይ! የለም አይጎበኙኝም፣ ፊታቸውን ካየሁ 15 ዓመት ሆኖኛል›› አለው፡፡ አባ ኪሮስም ማንነቱን በደንብ እንዲነግረው ሚሳኤልን ለመነው፡፡ ድኃው ሚሳኤልም ‹‹አባቴ የኬልቄዶን ንጉሡ እናቴም የራሕራሕ ንጉሥ ልጅ ናት፡፡ አባቴ ሆይ ዕውነት እልሃለሁ በአባቴ ቤተ መንግሥት አገልጋዮቹ ወርቁን፣ ብሩን በእግሮቻቸው ይረግጡታል›› አለው፡፡ አባ ኪሮስም ‹‹ወደዚህ ገዳም ማን አመጣህ?›› አለው፡፡ እርሱም ‹‹እንደ አንተ ያሉ ሁለት ሰዎች በአባቴ መጥተው ባደሩ ጊዜ በእኩለ ሌሊት ፊቱ ብሩህ የሆነ ሰው ወደኔ መጥቶ ‹ሚሳኤል ሆይ ሲነጋ ተነሥተህ ከእነዚህ ሰዎች ጋር ሂድ› ሲለኝ እኔም ወጥቼ ከዚህ ቦታ ደረስኩ›› አለው፡፡ አባ ኪሮስም የአባቱን የአባ በብኑዳን ታሪክ ለሚሳኤል በመንገር አጽናናው፡፡

ከዚህም በኋላ አባ ኪሮስ በጽኑ ሕማም የተያውን ሚሳኤልን በሞት ያሰናብተው ዘንድ ወደ ጌታችን ለመነ፡፡ ጌታችንም እልፍ አእላፍ ቅዱሳን መላእክትን አስከትሎ ተገለጠለትና ‹‹ወዳጄ ኪሮስ ሆይ ጠርተኸኛልና መጣሁ›› አለው፡፡ አባ ኪሮስም ‹‹ጌታዬ ሆይ ይህ ሰው ሕማም በዝቶበታልና ያርፍ ዘንድ አናብተው›› ብለ ጌታችንን ለመነው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወዳጄ ኪሮስ ምን ያህል እንደምወድህ የመላእክት ሠራዊት ያዩና ያውቁ ዘንድ ይህን በሕመም በተያዘው ወዳጄ ላይ ጣለው›› ብሎ በእጁ የያዘውን የገነት ተክል አበባ ለአባ ኪሮስ ሰጠው፡፡ አባታችንም ያንን የገነት ተክል አበባ ከጌታችን እጅ ተቀብሎ በሚሳኤል ፊት ላይ በጣለው ጊዜ ወዲያውኑ የሚሳኤል ቅድስት ነፍሱ ያለ ምንም ፃዕር ወጣች፡፡ ጌታችንም ያችን ቅድስት ነፍስ ተቀብሎ ሳማት፡፡ ከእርሱም ጋር በብርሃን ሠረገላ አስቀመጣት፤ አውጥቶም በሰማያዊ ክብር አኖራት፡፡

ከዚህም በኋላ አባ ኪሮስ ወደ ገዳሙ አበ ምኔት ሄዶ ድኃውን ይቀብሩት ዘንድ ለመነኮሳቱ እዘዝ አለው፡፡ አበ ምኔቱም በመታጀር ‹‹ምን ግዴታ አለብኝ?›› አለው፡፡ አባ ኪሮስም ባስጨነቀው ጊዜ ሰባት መነኮሳትን አዘዘለት፡፡ እነርሱም መዕጠንታቸውን ይዘው ሲነሡ በዚህ ጊዜ አባ ኪሮስ ‹‹የሚያጥኑት አሉና የረከሱ ማዕጠንቶቻችሁን አስወግዱ ነገር ግን ዝም ብላችሁ ቅበሩት›› አላቸው፡፡ በዚያም ጊዜ አራቱ የመላእክት አለቆች የቅዱስ ሚሳኤልን ሥጋ ሲያጥኑት መዓዛው ገዳሙን መላው፡፡ መነኮሳቱም ‹‹ይህ የሚሸተን እጅግ የሚጥም መዓዛ ምንድነው? ወይስ ይህ መነኩሴ ሥራይን ያውቅ ይሆንን?›› ተባባሉ፡፡ የቅዱስ ሚሳኤልንም ሥጋውን ወስደው ከቀበሩት በኋላ ከመቃብሩ ጠበል ፈለቀና ለብዙ ሕሙማን ፈውስ ሆነ፡፡

አባ ኪሮስም የአባ ሚሳኤልን ክብር ለእነዚያ ግብዝ መነኮሳትና ለአበ ምኔቱ በነገራቸው ጊዜ ፈጽመው አዘኑ፡፡ ከአባ ኪሮስ እግር ሥር ወደቀው ‹‹ይቅር በለን›› ባሉት ጊዜ እርሱም ‹‹በአባ ሚሳኤል መቃብር ላይ ወድቃችሁ እርሱን ይቅር በለን በሉት›› አላቸው፡፡ እነርሱም አባ ኪሮስ እንደነገራቸው ባሉ ጊዜ ‹‹በእናንተ ምክንያት ወደ መንግሥተ ሰማያት ገብቻለሁና እግዚአብሔር ይቅር ይበላችሁ›› የሚል ቃል ከአባ ሚሳኤል መቃብር ሰሙ፡፡

የአባ ኪሮስ የአባ ሚሳኤል ረድኤት በረከታቸው ይደርብን በጸሎታቸው ይማረን!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

18 Oct, 07:29


‹‹በመቃብሩ ላይ ወድቃችሁ ይቅር በለን በሉት››
👇👇👇

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

17 Oct, 06:48


ሦስት የምሕረት መፍሰሻ አንድ የይቅርታ ምንጭ።
🙏የለመለመ የምሕረት ምንጭ ለሚሆን ለአብ ምስጋና ይገባል።
🙏የለመለመ የሕይወት መገኛ ለሚሆን ለወልድ ሰላምታ ይገባል።
🙏የለመለመ የሕይወት መፍለቂቃ የሚሆን ለመንፈስ ቅዱስ ሰላምታ ይገባል አሜን።
#ሰይፈ_ሥላሴ
ሥላሴ ይክበሩ ይመስገኑ! አሜን!!!

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

17 Oct, 06:39


☞ይቅርታቸው ሀብታቸው ረድኤታቸው በወዳጃቸው በህዝበ ክርስቲያኑ ላይ
ይደርና፡፡የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተአምራቸው ይህ ነው፡፡
☞የአብ የወልድና የመንፈስ ቅድስን መታሰቢያ የምታደርግ አንድ ህፃን ያላት
ሴት ነበረች፡፡
☞ከዕለታት በአንድኛው ቀን ይቺ ሴት ለሥላሴ መታሰቢያ እንጀራ የምትጋግርበት
ደረቅ እንጨት ፈልጋ ባጣች ጊዜ ያን ሕፃን ልጅዋን ውድ ልጅዋን ውድ ልጄ ሆይ
ባደግህ ጊዜ የምትከፍለው ደረቅ እንጨት በመፈለግ ብዙ ደክሜ አጥቻለሁና
አለችው፡፡
☞ሕፃኑም መልሶ መልካሟ እናቴ ሆይ ሁሉንም ነገር ተይው ይቅር ብዙውን
አትድከሚ ነገር ግን ሥላሴ ያው ቁልናል አላት፡፡
☞ይህን ከተባባሉ በኃላ ዳግመኛ እናቱን ጠራትና እሰኪ ተነሽና የመጣልሽን
ተመልከቺ አላት፡፡
☞ልሳነ መብረቅ በሆኑ መላዕክት እጅ የተዘጋጀ እንጂ በሰው እጅ የተጋገረ
ያይደለ የትኩስ እንጀራ መዓዛ ሽታ በዚህ አዳራሽ ውስጥ ይሸተናል አላት፡፡
☞ይህንንም በሰማች ጊዜ ፈጥና ወደ ቤት ገባችና መዓዛው ወይም ሽታው
የሰውን ልብ እጅግ አድርጎ የሚስደስት እንጀራ በመሶብና በገበታ ላይ ተሰርቶ
አገኘች ሰዎችም ከመዓዛው ጣፋጭነት የተነሣ በሽታው ብቻ እንደበሉ ሆነው
ጠገቡ፡፡
☞በዚያም ጊዜ ዘመዶችዋን ጉረቤቶችዋን ጠርታ ወዳጆቼ ሆይ በቤቴ ውስጥ
የሆነው ሥላሴ ያደረጉት ድንቅ ሥራ ኑና ተመልከቱ አለቻቸው፡፡
☞ሀገሩም ሰዎች ለደጋጎቹ ወዳጆቻቸው የሆነውን ሥልሱ ቅዱስ ያደረጉትን ድንቅ
ሥራ ተመልክተው አደነቁ በታላቅ ደስታም እየተደሰቱ በአንድነት ወደ አዳራሹ
ገቡ፡፡
☞ከዚያም በኃላ የሀገሩ ሰዎች ሁሉ ሥልሱ ቅድስ ሰዶም ገሞራን ያጠፈፋበት
ጥር 7ቀን ምክንያት በማድረግ እንደዚያች ሴት ሁሉ በየራሳቸው የአብ የወልድ
የመንፈስ ቅዱስን መታሰቢያ ማድረግ ጀመሩ፡፡
☞እንሆ ነዳያን ችግረኞችን እየጠሩ ከተዘጋቸው ምግብ አብልተው አጠገቧቸው፡፡
የመጡትን ሁሉ እየጋበዙ አሰደስቷቸው፡፡
☞በአሥራ ሁለቱ ወር በየግል ቤታቸው የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ
የበዓላቸውን መታሰቢያ የሚያደርጉ ሆኑ ይልቁንም በጥር 7በሐምሌ 7ቀን
ያለማጓደል በፍጹም ትጋት ይዘክሩ ጀመር፡፡
☞ይቅርታቸው ሀብታቸው ረዲኤታቸው ከህዝበ ክርስቲያኑ ጋር ለዘለዓለሙ
ይኑር፡፡ አሜን፡፡
☞(የማክሰኞ ሰይፈ ሥላሴ)

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

17 Oct, 06:39


☞ይቅርታቸው ሀብታቸው ረድኤታቸው በወዳጃቸው በህዝበ ክርስቲያኑ ላይ ይደርና፡፡
የአብ የወልድ የመንፈስ ቅዱስ ተአምራቸው ይህ ነው፡፡
👇👇👇👇

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

16 Oct, 08:11


ጆሮ ያለው ይስማ‼️ ልብ ያለው ልብ ይበል‼️

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

14 Oct, 08:25


https://youtu.be/LlsanPFoRZw?si=QlYakqENHp9FaHvT

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

13 Oct, 08:56


ጆሮ ያለው ይስማ‼️ ልብ ያለው ልብ ይበል‼️

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

13 Oct, 06:44


👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት አምስት የተወሰደ
ተጻፈ በ21/01/2004 ዓ.ም

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

13 Oct, 05:58


https://youtu.be/hCP9QvvPHuY

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

11 Oct, 11:15


https://www.youtube.com/watch?v=c-Qp3cEeC6A

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

11 Oct, 11:12


https://www.youtube.com/watch?v=t9iNpTO0OrQ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

11 Oct, 11:12


https://www.youtube.com/watch?v=AsNvdujMmTI

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

09 Oct, 07:32


🟢🟡🔴
መስከረም 29 | #ቅድስት_አርሴማ #ከእመምኔቷ_ከአጋታ እና ሌሎች ደናግላን ጋር በሰማዕትነት ዐረፈች፤

● #ቅዱስ_ዮሐንስ_ነባቤ_መለኮት (ወንጌላዊው) እንደ ንስር መጥቆ "ቀዳሚሁ ቃል..በመጀመርያው ቃል ነበር" (ዮሐ. ፩፥፩) ብሎ ወንጌሉን የጻፈበት ዕለት ነው።

˙ •🌼• [ ስንክሳር ዘመስከረም ፳፱ ] •🌼

•• ቅድስት አርሴማ ሰማዕት ••
๏-❀-๏

በዚችም ቀን ከቅድስት አርሴማና ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት ዐረፉ።

ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ።

ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ።

እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።

ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።

ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።

የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።

ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።

አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።

ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።

🌿🌼🌿

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

09 Oct, 07:32


🟢🟡🔴
መስከረም 29 | #ቅድስት_አርሴማ #ከእመምኔቷ_ከአጋታ እና ሌሎች ደናግላን ጋር በሰማዕትነት ዐረፈች፤

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

09 Oct, 07:19


የእህታችን እህተ ማርያም እጅግ ድንቅ ምስክርነት
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህርዳር
28/1/2017

👉 በስማቸው ዘካሪና ፅዋ ጠጪዎች በሰላሙ ጊዜ ወደ ፈጣሪያቸው የተመለሱ የኢትዮጵያ ዓለም ብርሃንን ምክር ድምጽ
የሰሙና የተገበሩት ፤ ሁሉም ቅዱሳን ሊቃነ መላእክት ድንግልም ሁሉም ሰማእታት ቅዱሳን ወዳጆቻቸውን በሥላሴ ፊት
አቅርበው ማልደው ለታመኑባቸው ለወደዷቸው ሁሉ ምህረትን አስገኝተዋል ፡፡ በዚህም መሰረት ለወዳጆቻቸው
በየግንባራቸው ላይ ምልክት ተደርጓል ፡፡ ይህንን የሚያዩት ለቁጣው ጠረጋ እሳት ለብሰው እሳት ጎርሰው ምድርን
እያንቀጠቀጡ የሚመጡት ቀሳፊ መላእክት መቅሰፍትን ያዘሉ ፍርድና ትእዛዝ ፈፃሚዎች ተግባር ላይ ሆነው ያለ ምሕረት
ምልክት አልባ የሆኑትን እንደተፈረደባቸው እንደተወሰነባቸው እንደታዘዘባቸው የአፈፃፀም እርምጃ ሲያከናውኑ ሲያዩ ብቻ
ነው ፡፡

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት አስር ገጽ 30 የተወሰደ

የተዋህዶ አርበኞች-Ye Tewahedo Arbegnoch

09 Oct, 07:19


የወንድማችን ገብረ መድህን እጅግ ድንቅ ምስክርነት ፩
ከቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ = ባህርዳር
28/1/2017

👉 በኢትዮጵያ የሚነግሠው ንጉሥ ደግሞ ንጉሠ ነገሥት ቴዎድሮስ ነው። 
ይረዱት፤ ጊዜውም አልቆ እደጃቸው የደረሰ ነው።

👉 ከኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክት ዘጠኝ ገጽ 7 የተወሰደ