ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]• @ktebiban_meder Channel on Telegram

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

@ktebiban_meder


°| ከአፍቃሪያን ገጽ በፍቅር ቀለም |°

•[ ከጠቢባን ምድር! ]•
🌴 دار الحكمآء

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]• (Amharic)

በአፍቃሪያን ገጽ ላይ በፍቅር ቀለም እየጠቢባነት ያለ አዝናኝ ምድር ከጠቢባን ምድር ሆነን ለራስ አብዱ ሩሚ ትንሽ ለመሆን የሚችል ተግባር። የራስ አብዱ ትንሽ በሆነው በዓለም ላይ ብቃት እንዲሆን አፈር ብሎአል። እስኪ መግባት ስሚዎችም ለምስል ካደንም በላይ አይዘወት እያጠቡ ስልኩ በሞኝ ምድር እንቆማለን። ከጠቢባን ምድር ከቤቶቻችን እንጠቀማለን።

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

13 Feb, 18:23


የይቅርታ ለሊት!

አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ💚

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

13 Feb, 13:52


#ሸዕባን_አጋማሽ_ምን እንስራ?

የሸዕባን አጋማሽ ለሊት የሚውለው ሐሙስ ለጁምዓ ለሊት ነው። በዚህ ለሊት አላህ ፍጡራኑንን ኹሉ በጅምላ የሚምርበት ለሊት ነው። ከሁለት ሰዎች ሲቀር አንደኛው፦

* አላህ ላይ የሚያጋራና
* በልቡናው ውስጥ ቂም የሚቋጥር ሰው

አላህ ላይ ማጋራት ሲባል ይህ በየሜዳው በኾነው ባልኾነው አጋርተኻል እንደሚባለው ሰበካ ሳይኾን። የፈጣሪን ችሎታ ለፍጡር፣ ቁስና፣ ሰበብ መስጠት ኹሉ የአጋሪዎች ተግባር ላይ ሊገኝ ይችላል።

ሁለተኛው የጥላቻና ቂምን በተመለከተ ሁላችንም የምንፈተንበት አጀንዳ ነው።

በዚህ ለሊት የተለየ የሚሰራ የተደነገገ አምልኮ የለም። ለዚህ ለሊት የሚያስፈልገው ከተጠቀሱት ሁለት ተግባራት የጸዳ ልብ ማዘጋጀት ነው።

ይህን ንጹሕ ልብ ማዘጋጀት ከባድ ስለኾነ መማጸኑ ይሻላል ብለው ይመስለኛል ዑለሞቹ ምሽቱን በሙጥለቅ አምልኮዎች ያሳልፉታል። ሙጠለቅ አምልኮ ማለት በየትኛውም ቦታና ጊዜ ማድረግ የሚቻል የአምልኮዎች አይነት ናቸው። ለምሳሌ ቁርኣን፣ ዱዓ፣ ሰለዋት በየትኛውም ሁኔታ ቢሰሩ ክልከላ የሌለባቸው ጉዳዮች ናቸው። በዚህም በ 15ኛ የሸዕባን ለሊት ዑለሞቹ የያሲንን ምዕራፍ ከዱዓዎች ጋር ያከናውናሉ። ይህ የግዴታ አምልኮ ሳይኾን ከዕውቅ ዑለሞች የተገኘ ተጅሩባ ነው። በምሽቱ የሚደረገው ይህ የዱዓ መርሀግብር የአላህን በዚህ ለሊት ያዘጋጀውን ልዩ ሽልማት ለመጎናጸፍ የሚደረግ ተማጽኖ ነው።

አላህ ይወፍቀን

ልባችንን ያጽዳልን

© Best Kerim ©

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

13 Feb, 13:51


የልብ ጉዞ~14
:
በሙተሰዊፎች ዘንድ ወደ አላህ በሚደረግ ጉዞ ላይ መነሾና ዋነኛ መስፈርቱ የሩህ ሸይኽን ማግኘት ነው። ነፍስያን ከአማራ ቢሱዕ(ወደ መጥፎ አዛዥ) ወደ ለዋማ (ራሷን ወቃሽ) እየአደበ ቀስ በቀስ የሚያሳድጋት ሙረቢ ያስፈልጋታል።

ቀደምቶች የሙረቢን ወሳኝነት ተረድተው ብዙ ቦታዎችን የሩህ ሸይኻቸውን ፍለጋ ያስሱ ነበር።
ለዚህ ነው ሰይዲ ኢማም አቡ ሀሰን አል-ሻዚሊይ(ቀሲ) ከቱኒዚያ ተነስተው ሚስርና ኢራቅን ያዳረሱት። ኢራቅ ሲደርሱ ሸይኻቸው ሰይዲ አብድሰላም ኢብኑ በሺሽ(ቀሲ)  በመግሪብ(ሞሮኮ) እንደሚገኙ ተነግሯቸው ዳግም የተመለሱት።
ይህን ያህል ሀገራትን ወደ አላህ የሚያደርሳቸውን ሸይኽ ፍለጋ ይጓዙ ነበር።

ሙርሺድ እጅግ ድብቅና እንዲሁ ማይገኝ ከንዝ ነው። ሙርሺዱን ያገኘ ትልቅ ድልብን አግኝቶዋል።
የሀቂቃ ሙርሺድ ረባኒይ ከሆነ ካንተ ዱንያዊ ጥቅምን ቅንጣት ታክል የማይሻና በኢልም የተሞላ ነው። ምንም ነገርን ይሰጥሀል እንጂ ካንተ አይቀበልህም። የነፍሱን ጣጣ ጨርሶ ራሱን ለአላህ ፍቅር ያስገዛና ከኸልቁም ጋር በፍቅርና እዝነት የሚኗኗር ነው።
ወደ ቀጥተኛው መንገድና ኑር ወደሆነው አለም የሚያመላክትህ. . ለሀጃህና ችግሮችህ እጁን እያነሳ በዱዐ ሚያበረታህ ነው። በምንም አይነት እንቅስቃሴው ሸሪአን የሚጣረስ ድርጊትንም አያከናውንም።

ሙረቢ የሩህ አባት ነው። ነፍስን ከህፀፆ እያላቀቀ ወደ ከፍታ ማማ የሚዶላት። ወደ ብርሀን ጠቋሚ አመላካች ናቸው። ነፍስን በዚክር  ዝናብ እያጣጠቡ ከዕድፎቿ እንድትፀዳና ሙጥመዒን እንድትሆን የሚያደርጉ። ልብ ውስጧ ያሉትን መኽሉቅ ሁሉ አፀዳድታ በአላህ ፍቅር እንድትሞላ የሚያደርሰውን መንገድ አመላካች ናቸው።


እንዲህ ያለ ሸይኽን ያላገኘን እኛ በጠዋትና ማታ ዚክሮች ራስን መጥመድ አስፈላጊ ነው። ዊርድ ሊኖረን ይገባል። ለራሳችን በራሳችን ግድ ያደረግነውና ዘወትር የምናዘወትረው ተክራሩ የተገደበ ዚክር ማለት ነው። አላህ ዘንድ ተወዳጁ ስራ ትንሽም ቢሆን ዘውታሪ የሆነው ነው።
ልሳንን ከዚክር ጋር ማቆራኘትና ከነፍስ ክጃሎት ለመላቀቅ ሰለዋትና እስቲግፋርን መታጠቅ ያስፈልጋል።
የቀልብ ጡማዕኒና የሚገኘው አሏህን በማውሳት ነው። አላህን ያስታወሰ አላህ ያስታውሰዋል። አላህን መዘከር የልብ ጌጥ ነው። አላህን ማስታወስን ያዘወተረ ሰው ከጋፊሎች መዝገብ ይፋቃል። የልቡ ፅልመት እያተገፈፈ የልቡ ኑር ወገግ ይላል።
" ሸይኽ የሌለው ሰው ሶለዋትን ይያዝ። ሶለዋት ሸይኽ ይሆነዋል ይላሉ ሸይኾቹ። "

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

12 Feb, 19:18


አንድ ኢአማኝ የሆነ ሰው
" አላህ ማን ነው? " ብሎ ቢጠይቃችሁ : ምን ብላችሁ ትመልሳላችሁ?😊

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

12 Feb, 17:16


የልብ ጉዞ~13
:
ተሰዉፍ ፦ ተሰዉፍ አል-አዝዋቅ እና ተሰዉፍ አል-አኽላቅ
ተብሎ በሁለት ይከፈላል። ተሰዉፍ አል-አኽላቅ እጅግ ወሳኙና መሰረታዊው የተርቢያ ክፍል ነው። አኽላቃችን(ምግባር) ሳይገራ ወደ ዘውቅ መድረስ አይቻለንም። ብዙዎቻችን ተሰዉፍ አል-አኽላቅን ሳንሸጋገር ወደ ዘውቅ መድረስን እንሻለን። ምኞታችን እጅግ መሰረተ ቢስ ነውና ሀሳብችን እውን አይሆንም። ትልቅ መቃምን የከጀለ ትንንሽ ከሚመስሉ የልብ በሽታዎች መለቅለቅ ሊጀምር ግድ ይለዋል።
:
የተሰዉፍ መጀመሪያው ደረጃ "ተኽሊያ" ይሰኛል። ነፍስን ከእድፎቿ ማጥራት። ልብን ከህመሞቿ ማከምና ማዕሲያ ከተባለ ነገር ሁሉ ነፍስን ማራቅ። ልብን ባዶ ማድረግ። ነፍስያን ከዕልፍ መሻቶቿ አቅቦ ፍላጎቷን በባዶነት መሙላት።
ቀጣዩ ደረጃ "ተህሊያ" ይሰኛል።
ከማዕሲያና ከልብ በሽታዎች ኦና የሆነችን ነፍስ በመልካም ተግባርና እሳቤ መሙላት። ልብን በተቅዋና ተዋዱዕ ማስጌጥ። ነፍስን በበጎ ኒያ ማጠን።
ከአላህ ፍጥረታት ጋር በሙሉ በልስልስ ልብ መቅረብና የመልካም ምግባርን ኑር ማጥለቅ። ከልብ በሽታዎች በጠራችው ልብ ቦታ ላይ የልብ አምልኮዎችን መከረር።
የመጨረሻው ደረጃ "ተጅሊያ"
ኢማንና ተቅዋችንን ሚያጠናክርልን ከአላህ የሆነን ኢልም መሰጠት። በመናምና በተላያዩ ሁኔታዎች ላይ ወደ ሲራጠል ሙስጠቂም የተመራን እንድንሆን የሚያደርገን እገዛ ከአላህ ዘንድ የምንቸርበት መቃም ነው።

ብዙዎቻችን 'ተኽሊያ'  እና ' ተህሊያ' ን ሳንሸጋገር ወደ አለመ ተጀሊ መድረስን  እንሻለን። ልባችንን ከበዙ ፅልመቶቿ ሳናነፃት ፣ ነፍስያችን እንዳሻት እየጋለበችን ከተጀሊ ባለቤቶች መሆንን እንከጅላለን። የሀቂቃ መድረስ የምንፈልገውን ደረጃ ላይ መድረስ የምንሻ እንደሁ ከትንንሽ እርምጃዎች መነሳት ግድ ይለናል።
ልባዊ ህመማችንን መርምሮ ከህመሙ ለመታከም ከመጣር። ከዛም አላህን በሙሉ ልብ ሆኖ በመገዛት ነፍስን የአላህ ትዕዛዛት ላይ እንድትዘወትር ማድረግ። ከመዘውተርም አልፎ አላህን ማውሳትና በትዕዛዙ ውስጥ በመቆየት የልብ እፎይታን ማሰስ።
የሀቂቃ ከኢባዳችን የአላህን ውዴታ መከጀል። የኢማንን ጥፍጥና ልቦና ላይ ጠብ ያለች ጊዜ ጀሰድ ለድካም ቦታ አይተውም። ኢባዳ ላይ እጅግ ይበራታል። ዚክር እስትንፋስ ይሆነዋል። አላህን ማመፅ ሞት ይሆንበታል።
እነኚህን የተኽሊያና የተህሊያ መቃሞችን ከተሸጋገርን እንደ አላህ ፍቃድ ወደ ተጀሊ መድረሳችን አይቀሬ ነው።

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

11 Feb, 14:35


የልብ ጉዞ~12
:
የልብ ንፅህናን ነፍስን አደብ ስለማስያዝና ምግባርን ለመግራት የሚጣርበት የኢልም ዘርፍ 'ተሰዉፍ' ነው።
ተሰዉፍ ውስጥ በሸሪዓ ድንጋጌ ዋጂብ ወይም ሱና የሆኖ የተለያዩ አምልኮዎች ሩህ እንዲኖራቸ ያደርጋል።
የነፍስ ታዕዲብ ከሌለ በስራችን መኩራትና ነፍስን የመኮፈስ በሽታ ይጠናወተናል። ሀቂቃ ባርነታችንን ረስተን ራሳችንን ከጀነቱ አፀድ እንደተደላደልን አድርገን እናስባለን። ምንምነታችን ይሰወረናል።

አምልኮዋችን ከጀሰዳችን ያላለፈው..ልብ ላይ ጠብታ ጡማዕኒን የማይሰጠን በነፍስ እስር ላይ ስላለን ነው።
አላህን በድብቅ ሆኖ የማንሾካሾክን ጣዐምን ያጣነው ጣዕሙን ብቻ ሳይሆን ማንሾካሾኩንም የምንነፈገው በኢባዳችን ስንዳነቅና የሌሎችን ማንነት አሳንሰን ራሳችንን ከሁሉም እሻላለሁ በሚል ባዶ እብሪት ስንነፋፋው ነው።

በኢልመ ተሰዉፍ የተገራች ነፍስ ባለቤት የሆነ ሰው ከእርሱ በእድሜ ያነሰን ሰው ሲያይ " እርሱ እንደኔ ብዙ አመታትን አላህን አላመፀም።  ይሀው እኔ ለአመታት አላህን ሳምፅ ኖሪያለሁ። በማመፅ እበልጠዋለሁና ከኔ እርሱ ይሻላል" ይላታል ነፍሱን።
በእድሜ ከእርሱ የተለቀን ሰው ሲያይ " እርሱ ከኔ የተሻለ አውቆዋል ፣ ፆሞዋል ከኔም በላይ ሰግዶዋልና ከኔ ይሻላል " እያለ የሀቂቃ ሩሁን ተዋዱዕ እንዲኖራት ያደርጋል። በወንጀል ላይ የተዘፈቀን ሰው ሲያይ እኛ እንደምናደርገው ማንቋሸሽና የጀሀነም ብሎ በመፈረጅ ነፍሱን ከእሳት አያጠራትምና እንዲህ ይላል
" እርሱ ተውበት አድርጎ ኻቲማው ሊያምርለት ይችላል። የኔስ ኻቲማ ቢበላሽ ምን አሳወቀኝ?" ይላል
ሁሌም ምንምነቱን እያወጀ የአላህን ፍቅር ይማፀናል።

ተሰዉፍን ተዕሪፍ እንዳደረጉ አካቢር አሊሞች
" ሱፊይ ማለት ቀልቡ የጠራ፣ የሙስጠፋን መንገድ የተመራና እርሱ ዘንድ ድንጋይና ወርቅ እኩኩል የሆኑበት ነው " ይላሉ ኢማም ጁነይድ(ቀሲ) 'ይመስሉኛል'።

ዛሂድ ማለት ዱንያን የማይመልክ(የማያካብት) ፣ ሀብት ንብረት የሌለው ሳይሆን ዱንያ የማትመልከውና የማትገዛው ነው። በዚህ ግንዛቤ ልባችን ውሥጥ የፍቅሯ ዘር ስር እንዳይዝ ጥፍጥና ቆራጩን ሞት ማስታወስን ማዘውተር ያስፈልጋል። ለነፍሱ የሚሰጋ ሰው ወደ መድህን መንገድ የሚያደርሰውን እርምጃ ከማድረግ አይወገድም። ራህመቱ በስራችን ልክ ነውና ሚከፋፈለን ምን ስራ አለን? ልባችን ውስጥ ጠብታ ፍቅር አለ? እውነታውን ከራሳችን ሳንሸሽግ እንመልሰው። መልሳችን ለልብ እርምጃ መነሾ መሰረት ይሁነን።

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

10 Feb, 17:24


ይህች እፍኝ ህይወት ሁሌም ከጥንድ ነገራቶች የተሰፋች ናት። ብርሀን ካለ ጨለማ ፣ ደስታ ካለ ሀዘን . . ውድቀት ካለም ከፍታ ይቆራኘዋል። ሁሉም ከተቃራኒው ጋር ጥንድ ሆኖ ይገኛል።

  ትዝ ይለኛል ገና በልጅነቴ የአካልና፡ የምግባሬም አሳዳጊ የሆነችዋ እናቴ . .
"አሱር" ሰገድክ? ብላ የጠየቀችኝ ዕለት።
በጨዋታ የዛለ አካሌን ከፊቷ ሰይሜ
"ሰግጃለሁ! " ብዬ ስቀጥፍ ፡ ምንም እንኳ እየዋሸኋት እንደሆነ ቢገባትም ፡ ፈገግ ብላ
" ችግር የለውም ፡ እርሱ እንደሁ ያይሀል! " ብላ የመለሰችልኝን አልዘነጋውም።

" እርሱ እንደሁ ያይሀል! " ልቤ ላይ ቀረች። ነፍሴ ያቺ ትንሽ ገላዬ አልበቃ ብሏት ተወራጨች። እየተቻኮልኩ ውዱዕ ላደርግ ውሀ መቅጃውን ፍለጋ ስራሯጥ አይኔ ላይ ተስሎዋል። የእናቴ ለሳቅ የቀረበ ፈገግታም ልቤ ላይ በደማቁ ተከትቦዋል። አንዳንዴ አሁን ላይ ያሉ ዳዒዎች ምናለ ከእናቴ የማስተማርን ጥበብ ቢማሩ ብዬ አስባለሁ።

ከዛ ዕለት ቡኋላ " እርሱ እንደሁ ያይሀል። " የህይወቴ መርህ ሆነ። ብዙ የጥፋት በሮች ሲከፈቱልኝ ፡ መከርቸሚያ ቁልፌ ነበር። የውድቀት ታሪኬ እንዳይፃፍ ፡ የሚያፀናኝ ብርቱ ቃል!

| ከኪሚያ የተወሰደ . . . ! |

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

10 Feb, 13:37


የልብ ጉዞ~11
:

   ሸሆቹ  5ተኛዋን ነፍስ  ••نفس الملكوتية••    መለኮታዊ\መላእካዊ  ነፍስ    ይሏታል።   ከመላእክት  ነፍስ ጋር እጅጉን ትመሳሰላለች።
       ይህች ነፍስ  ወደ ፍቅር፡መታዘዝ  ፡ፈጣሪን ወደ ማምለክ፡  ይቅርታ  ማድረግ  እና መሰል  ሰናይ ባህርያቶች የምታዘነብል  ምስጉን ነፍስ ናት።
      አሏህ መላዕክትን  አ •የአሯህማን ፍጹም ተገዢዎች • እንደሆኑ  °°ፈጣሪያቸውን የማያምጹ ባሮች°° ሲል  አወድሷቸዋል።
        ባለ ምስጉን ነፍስ የሰው ልጆችንም በዚሁ ገለጻ  ባህሪያቸውን ያስቀምጣል፡
     وَعِبَادُ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلَّذِينَ يَمْشُونَ عَلَى ٱلْأَرْضِ هَوْنًۭا
የአልረሕማንም ባሮች እነዚያ በምድር ላይ በዝግታ የሚኼዱ ናቸው። አል ፉርቃን




6ተኛዋ የነፍስ እርከን  ከሁሏም የላቀች እና  በውስጠ ነፍስ ጉዞ( ተሰዉፍ) ላይ ጥቂቶች እንጂ የማይደርሱባት ናት።••نفس القدسية•• የተቀደሰችዋ ነፍስ።

إذا خضعت نفسك الملكوتية
ترزق من الأعلى القدسية
መልዐካዊ ነፍስህን አዋድቀህ የጸናህ ግዜ
  ከልዕሉ ጌታ   የተቀደሰችዋን ነፍስ ትመነዳለህ


ِ يُلْقِى ٱلرُّوحَ مِنْ أَمْرِهِۦ عَلَىٰ مَن يَشَآءُ مِنْ عِبَادِهِ፡
የመገናኛውን ቀን ያስፈራራ ዘንድ ከባሮቹ በሚሻው ሰው  ላይ ከትዕዛዙ መንፈስን (ራእይን) ያወርዳል፡፥አል ጋፊር 

ይህች ነፍስ የኡርፋኖች ነፍስ ናት።የጌታዋን የላይኛው ዐለም ግዛት ትቃኛለች፡ከፍጥረታት የራቁ ሥፍራ እና ጥበቦችን ትጎበኛለች፡አሯህማንም ከምስጢር ጽዋ ላይ ይቀዳላታል፡  ከሰዎች ልብ ላይ ያለውንም ያስነብባታል። ከዚያም አልፎ ከሩቁ ዐለም ገብታዎች ያቋድሳታል

  እንዲህ አይነቱ የነፍስ እርከን ላይ ስለደረሱ ሙተሰዊፎች ሲወራ  የተባለው ታወሰኝ፡
      
إذا قعدت من العلماء ٱحفظ لسانك
  إذا قعدت من العارفين ٱحفظ قلبك

ከሊቃውንት ጋር ስትቀማመጥ ምላስህን ጠብቅ
ከ (ውስጠ ዐለም) አዋቂዎች ጋር ስትቀማመጥ   ልብህን ጠብቅ ።
       
ይህንን አርዕስት ካሰፋነው  ከማንወጣበት ባህር ይከተናልና  እንለፈው። ይህች የተቀደሰች  ነፍስ አጥናፈ ዐለማትን ሁላ ብታካልልም አንድ የማታልፈው ድንበር አላት።  ••ሲድረተል ሙንተሃ•• ያኔ ትላለች  ••የኔ መቃም እዚህ ጋር ያበቃል••
   አንዲት ገደበ ያልተበጀላት ነፍስ ስትቀር  የሐቢቡሏህ አህመድ  صلى الله عليه وسلم

  
   ነፍስ  ከዚህ ሁላ ውጣ ውረድ እና ትዕግስት የሚፈታተን ጉዞ በኋላ  እረፍትን ትሻለች። 7ተኛዋ ነፍስም ይህንን እረፍት  የምታስከጅልህ ነፍስ ናት።••نفس الجمادية••  ግትራዊ/ኢ ተንቀሳቃሽ ነፍስ ።

  ይህች ነፍስ  ከፍታን የማትሻልህ ፡ከአንድ ምስጉን የነፍስ እርከን ወደተሻለው እንዳታልፍ የምትጎተጉትህ ናት።
  በቅ አሏህኮ ካንተ ምንም አይፈልግም።ከዚህ በላይ ምን ፈለግህ?  ትጾማለህ  ትሰግዳለህ።መልካምን ታደርጋለህ። እስኪ  ንገረኝ ከዚህ በላይ ምን መሆን ፈለግህ?  እያልች ከፍታ ላይ እንዳለህ ታሳምንሃለች! ጥቂቶች እንጂ አያሸንፏትም!!!
                      ዋ እርሷን ያለፈ መጽደቁ ምንኛ አማረ!

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

10 Feb, 10:28


❤️❤️

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

09 Feb, 13:42


የልብ ጉዞ~10
:
ትንንሽ ና ብልጭልጭ ጊዜያዊ በሆኑ ነገሮች መባከን ምትፈልገዋን ነፍስ  . . .
ዋ ነፍሴ!  ስንቱን አከሰርሽው
ስንቱንስ  በርትተሽ  ከአሏህ ደጃፍ አደረስሽው

ሐቢቡሏህ ••من عرف نفسه عرف ربه•• ነፍሱን  ያወቀ ጌታውን አወቀ ያሉት  ለምን ይሆን?
ኦ አንቺ የምስጢር ጎተራ  ግዛትሽ ድንበር የለውም

ሰይዲ አባ የዚድ አል በስጣሚ ጌታውን ጠየቀው 
°°يا رب كيف الوصول إليك°°
ጌታዬ ሆይ  ወዳንተ መዳረሻው እንዴት ነው 
    አሏህም መለሰለት
      °°ٱترك الهوى وتعال°°
ስሜትን ተዋት   ከዚያማ  ወደኛ ጉዞህን ጀምር

ለዚህም ነው የሱፊ ሳዳቶች ስንኝ የቋጠሩት
°°من كان له هوى
               فليس له دوى°°
ያሸነፈው ስሜት
        የለውም መድሃኒት

  ሰይዲ ኢብን አጧእ አል ኢስክንድሪይ  ይህንኑ ሲያጠናክሩ  ያሉትን ከልብህ አኑር፥
           مكتوب على حضرة مليك القدوس
                   لا يدخلها أرباب النفوس
በጌታችን በቅዱሱ ሐድራ ላይ ተከትቧል!
   የነፍስ ተገዢዎች ደጃፌን አይዘልቋትም!
:
   ግን ነፍስ ምንድናት???
  ነፍስህ ማለት ከሩቅ ዐለም ሃይል ናት ፡ስጋህ ላይ ህይወትን የምትዘራ!

    ሊቀ-ሊቃውንቱ  የነፍስን አይነትዎችን ሲከፋፍሉ  በብዛት ይሰድሯቸዋል!     ጠቅለል ሲያረጓቸው ግን  ይላሉ   °°አንተ በውስጥህ ሰባት አይነት  ነፍሶችን አንግበሃል°°

በውስጥህ አንዲት ነፍስ አለች።ሲርብህ  ምግብን የምትሽልህ  ሲደክምህ  እረፍትን የምታስከጅልህ፡አጠቃላይ ስሜቶችህን የምታስተናግድባት ነፍስ   ••ነፍሱ ነባቲያህ••  ትባላለች።

ሌላኛዋ ነፍስ  የበላይነትን የምትፈልገዋ  ስሜታዊ ነፍስ ስትሆን   በሁለት ትከፈላለች 
                 ••نفس إبليسية ••
ሰይጣናዊ ነፍስ     ምዕናባዊ በሆኑ እኩይ ስሜቶች ትገፋፋሃለች።  የስልጣን  ፍቅር፡ የእዩልኝ አባዜ  የበላይነት ፍላጎት እና  መሰል እኩይ ባህርያት   የሷ ጉትጎታ ውጤቶች ናቸው።

ሁለተኛዋ የስሜታዊ ነፍስ ምድብ ደግሞ  ••نفس حيوانية••   እንስሳዊ ነፍስ    ስትሆን።ብላ ጠጣ  ዘንጥ   ተኛ   እና መሰል  ከስጋ ጋር የተገናኙ ስሜቶች የሚስተናገዱባት  የነፍስ አይነታ ናት።

    4ተኛዋ የነፍስ እርከን  ••نفس السبعية•• ትባላለች።በእኩይ ስሜት ጫፍ ላይ ስትሆን የምትገነፍል እንስሳዊ  ነፍስ ናት።
በቁጣ ግዜ እንደ አንበሳ በ2እጆችህ ጠረጴዛ ስትደበድብ፡
  በክርክር ግዜ እንደ አህያ ከፍ ባለ ድምጽ ስትንጫረር
    ፥በንዴት ወቅት እንደ እባብ ምራቅህን ስትታፋ
                ይሄኔ  •አውሬያዊ ነፍስ• ከበላይህ ሆና እየጋለበችህ መሆኑን አትዘንጋ።

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

08 Feb, 04:23


| 'አንተ'ን ብዬ በ'አንተ' ልርጋ! |

ሸግዬ ቀን ይሁንላችሁ💚
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

07 Feb, 14:32


የልብ ጉዞ~9
:

" ልቡ ውስጥ የብናኝ ያህል ኩራት ያለበት ሰው ጀነት አይገባም" ሀቢበሏህ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም።

ልብ እንድትጥራራ ከበሽታዎቿ መታከም አለባት። ብዙ ጊዜ በመልካም ስራ ላይ የሚከሰትና ብዙ ማይስተዋል ከባድ በሽታ ነው። 'ኩራት'
ሰይዲ አቡ የዚድ አል ቡስጣሚይ " አንድ ሰው በማህበረሰቡ ውስጥ  'ከእኔ የባሰ መጥፎ ሰው አለ' ብሎ የሚያምን ከሆነ ኩራተኛ ነው።" በማለት የኩራት ድካውን ያሳዩናል።

ዳውድ አጥ-ጣዒ በአንድ ወቅት "አምባ ገነን መሪዎች ዘንድ በመግባት በመልካም ያዘዛቸውና ከክፉ የከለከላቸው ግለሰብ ምን ሊደርስበት ይችላል?" ተብለው ተጠየቁ
"ግርፋትን እፈራለታለሁ" ሲሉ መለሱ። "ግለሰቡ ይህንን መቋቋም ከቻለስ " ሲባሉ "በሰይፍ እንዳይቀላ እሰጋለታለሁ " አሉ። "ይህንንም ለመቀበል ከተዘጋጀስ "
ሲባሉ። እንግዲያውስ ብዙ ሰው ሊያመልጠው የማይችለውን አደገኛ በሽታን ተናገሩ " ድብቁን በሽታ እፈራለታለሁ ! ራስን የመኮፈስ በሽታ።" ሲሉ መለሱ

የመኮፈስ ስሜቱን የገደለ፣ እኩይ የነፍሱን ዝንባሌ ያከሰመና ልቡን ከአረሞቿ አጥርቶ የአላህና መልዕክተኛውን ፍቅር በልቦናው ላይ የተከለ ሰው ከአለም ውጥንቅትና ጥፋት ተቋርጦ ወደ ሰማያዊው ብርሀንና ሰላም የሚያደርሰውን እስትንፋስ ይምጋል። ስቃይና መከራ ከሞላት ጀሀነም ርቆ ወደ እዝነቱ ጉያ ይጠጋል።
ራሳችንን ከልብ በሽታዎች የጠራን ነን ብለን ማሰባችን መታከም እንዳንችል ያደርገናል። ነፍሳችንን አናጥራት።
ስለ እዩልኝ በሽታ አብዳህ ኢብን አቢ ሉባባህ የተሰኙ አቢድ እንዲህ ይላሉ
" ለይዩልኝ በሽታ ከማንም በላይ ቅርብ የሚሆነው በሽታው የለብኝም ብሎ የሚያስብ ግለሰብ ላይ ነው።"

ነፍስ በብዙ አይነት እኩይ ክጃሎቶች የተሞላች ናትና ከመሻቶቿ ሸሽታ ወደ አላህ ትዕዛዛትና ፍቅር ልትሰናዳ ይገባታል። ለዚህም ነፍሳችንን ማወቅ በሽታችንን ለመለየትና የልብ ህመማችንን ለማከም ይረዳናል።

ስለ ነፍስ ምንነታና አይነቶቿ በቀጣይ ክፍሎች ምንዳስሰው ይሆናል። ( ቢአውኒሏህ)
___
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

07 Feb, 10:33


| ሙላ ጅስሜን አቃጥሎት የገራም እሳት ፡
እንደ ሀላጁ ፡ ይፈረድብኝ ስቅላት ፣
ብቻ ልቤን
ብቻ ቀልቤን የፍቅርህን ኑር አልብሳት!   |

[ አብዱ ሩሚ ]
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

07 Feb, 09:20


የሸዕባን ወር...



۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ ۚ
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا
۝

አሏህ በሰይደልዉጁድﷺ ላይ ሶለዋት እንድናወርድ ያዘዘበትን አያ በዚህ ወር ነበር የወረደው..

በሶላት ዐለ ነቢይ መከራዎች ይቀላሉ...ምኞቶች ይሳካሉ!!

اللهم صل وسلم وبارك على سيدنا محمد
قد ضاقت حيلتي فأدركني يارسول الله فأنت لها ولكل كرب


💢 ጁሙዐ ሙባረክ

© አህሉል ዊርዲ

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

07 Feb, 03:29


አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓለይህ❤️‍🔥

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

06 Feb, 15:55


የልብ ጉዞ~8

مزِّق القيدَ تَحرّر يا فتَى
كم ستَبقى مرهقًا حتّى متَى؟
-
جلال الدين الرومي

አንተ ሰው ነፃ ሁን ከእስርህ!
ለምን ያህል ጊዜ በእስር ትቆያለህ?

ጀላሉዲን አል-ሩሚይ!
:
አንዳንዴ ቆም ብሎ ማሰብ ይበጃል። ልብን ሰብሰብ አድርጎ በእርምጃ አጣጣላችን ኻቲማችንን ማሰቡ መልካም ነው። ምክንያቱም ሰው የሚሞተው በኖረበት ሁነት ላይ ነውና። በስሜትና በነፍስ ክጃሎት እስር ተጠፍንገን ባለንበት የሩህ ነፃነትን ማግኘት ማይቻል ነው።
የልብ ጭንቀት! ስክነት ማጣት. . .ጨለምላማ ነገርን ብቻ ማሰብ! ፍፁም የብቸኝነትና ራስን የመጥላት ስሜት ውስጥ የምንዘፈቀውም በነፍሳችን እስር ውስጥ ስንማቅቅ ነው።

ፍላጎቶቻችንን መግራትና ነፍስ ጌታዋ ባዘዛት ተግባራት  ላይ እንድትለምድና እንድትወድ ካደረገን ሰላማዊ ልብን እንታደላለን።

"ብርሀኑን ልቡ ላይ ያንጠለጠለ
ስለ አለም ጨለማ ግድ አይሰጠውም"
ይላሉ ጀላሉዲን አል~ሩሚይ

ልቡ ላይ የአላህን ፍቅር ያነገበ ሰው አለም ውጥንቅጡ ቢወጣ ሰላም ከርሱ ጉያ አትርቅም። በምንም አይነት ሀል ውስጥ ቢሆን ሰላም መረጋጋትና ተስፋ አይርቀውም። የልቡ ብርሀን ድቅድቅ መንገዶቹን እየከፋፈተለት በዱንያ ላይ ሰላማዊ ሀያትን ይታደላል። አኼራ ላይም ከሀድረተሏህ ደጀፍ ለመዝለቅ ከታጩት መሀል ይሆናል። እጅግ ታላቅ እድያ!!

የልብ ብርሀኑ የከሰመና ጥቁረት የወረሰው ሰው አለም በብርሀን ብታሸበርቅ እርሱ ዘንድ ያለው ግን ፅልመት ነው። ፈገግታ ለከውኑ ቢታደል ልቡ ላይ ሀዘን ድንኳን ቀልሶበታል። ዱንያ ላይ ያሉ ነገራቶች በጠቅላላ የልቡን ሰላም ማሰመለስ ይሳናቸዋል። እርካታ ያጣል። የመራራ ህይወትን ፅዋ ይጎነጫል።

ለልቡ ብርሀን ግንባሩን ከእግሩ ስር አኑሮ በሱጁዱ የልብ ጉዞውን ካላሰናዳ ወደ ሰላምና መድህን ደጃፍ ወደሚያሻግረው ድልድይ አይጠጋም።

" ከልብህ ላይ ጭንቀቶችህን ሁሉ ሊያሶግድልህ የሚችለው! የአላህ ሀይል ብቻ ነው "

ጀላሉዲን አል~ሩሚይ
_
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

06 Feb, 05:25


የልብ ጉዞ~7
:
ሙሀመድ ኢብን ዋሲዕ ኢማናዊ ዕይታቸው ጥልቅ የነበረ ግለሰብ ናቸው። የልብ ሰራተኞች እጅጉን ማነሳቸውን ባስተዋሉ ጊዜ " እኛ የአላህ ነን ወደርሱም ተመላሾች ነን" በማለት ያለቅሱ ጀመር። ያለፉ ወንድሞቻቸውንም አስታውሰው " ወይ ጓደኞቼ! ጥለውኝ ሄዱ .." እያሉ ያነቡ ነበር። ቤተሰቦቻቸው ግራ ተጋብተው " አባ ዐብደላህ ሆይ! አላህ ይዘንልህ ቀን ሚፆሙና ለይል የሚሰግዱ በአላህም መንገድ የሚታገሉ ወጣቶች እያሉ?" በማለት ሊያፅኗኗቸው ሞከሩ። መልሳቸው ግን እንዲህ የሚል ነበር " በርግጥም አሉ። ዳሩ ግን ሁላችንም በራስ መኮፈስ በሽታ ተጠቅተናል።" በማለት ተናገሩ።
:
ምንም ያህል የተቀደሱ ተግባራቶችን ብንፈፅም የልብ ንፅህና ከሌለን ተግባራችን ውድቅ ነው።
ለይል ሶላት እየሰገደ ኡጅብና ኪብር ከተጠናወተው ሰው ይልቅ የወንጀለኛ ሰው የፀፀት እህህታ አሏህ ዘንድ ይበልጥ ዋጋ አለው።

ሀቢባችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም " አላህ ወደ ቁመናቹም ሆነ ወደ መልካቹ አይመለከት። ነገር ግን ወደ ልባቹና ስራችሁ ይመለከታል። " ብለውናል።
ሀዲሱ ሚያመላክተንም የቀልብ መስተካከል የመድህን በር መሆኑን ነው። 
የተቅዋ ልባስ እየረገበ ከላይ ላይ ለ'እዩልኝ' የምንሰራት ስራ : ስራው ምን የገዘፈ ቢሆን አላህ ዘንድ ያላት ዋጋ ግን ከብናኝም ያነሰ ነው።
አላህ ዘንድ ዋጋ ከማጣት በላይ ምን ክስረት አለ?

ሀቢባችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እጅግ ከሳሪ ስለሆኑ ሰዎች ሲናገሩ ;
አንደኛው በጂሀድ ላይ ነፍሱን የሰዋ ሰው ነው። ምን እንደሰራ ሲጠየቅ በደም ከተነከረ አካሉ ጋር ራሱን ለአላህ ብሎ እንደሰዎና ለአላህ ብሎ ሲዋጋ እንደነበር ይናዘዛል። ግና ዋሾ መሆኑ ይጋለጥበታል። ሲዋጋ የነበረው " ጀግና! ደፋር " እንዲባል እንደነበር ይነገረዋል። መሻቱን ዱንያ ላይ ጨርሶዋልና ልፋቱ ከንቱ መሆኑ ተነግሮት ወደ ጀሂም ይሳባል። ሁለተኛው ቁርዐንን ሲያስቀራ ፣ ኢልምን ሲያስተምር የነበረ ሰው ለጥያቄ ይቀርባል። ምን እንደሰራ ሲጠየቅ " ለአንተ ብዬ እውቀትን አውርሽያለሁ። ቁርዐንን አስተምሪያለሁ" እያለ ይሰራው የነበረውን ስራ ይናገራል። ነገር ግን ልቡ ውስጥ የተሸሸገ የይሉኝ በሽታ ነበርና ለቅጣት ይታጫል።
ምፅዋትን ሚያበዛም ሰው ለጥያቄ ሲቀርብ። ለአላህ ብሎ እንደሰጠ ቢናገርም የልቡ ምስጢር ይፋ ሚሆንበት ዕለት ነውና የሸሸገው ይጋለጥበታል። "ሰጪ ተብለህ እንድትባል ነበር የሰጠሀው!" ይባላል። በስራው ላይ ጥርት ያለ ኒያ ለአላህ ያልነበረ በመሆኑም ለቅጣት ይዳረጋል።
:
እርግጥ ነው መልካም ስራን መስራት ለራህመቱ እንድንታጭ ያደርገናል። ግና ስራችን ሚመዘነው በልባችን ዕሳቤ ነውና የልብ ንፅህና ከምንም በፊት አስፈላጊ ይሆናል።
__
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

04 Feb, 14:01


የልብ ጉዞ~6
:
ሶስቱን በሮች ከቆላለፍን ቡኋላ በልቦናችን ላይ ፅልመት የሚያክለው "ኸዋጢር" ነው። ልብ ላይ ውል የሚል ሀሳብ። ይህ ሀሳብ ከሸይጣን ፣ ከነፍስያ ፣ አልያም ከመለክ ፣ ወይም ደግሞ ከአላህ ሱወ ዘንድ በኢልሀምነት የተላከ ይሆናል።

በልባችን የሆነ ሀሳብ ውል ሲል በሶስት አይነት ሚዛን መልካም ወይም መጥፎነቱን መለየት ይቻለናል። አንደኛው በሸሪዐ ሚዛን እናየዋለን። ሀራም፣ ሀላል ፣ ሙባህ ወይስ መክሩህ የሚለውን እንለያለን።
ሁለተኛው  በቀደም ሳሊህ ሰዎች ታሪክ ውስጥ ምንነቱን እናስሳለን።
ሶስተኛው በልባችን መሻት እኖስናለን። ልባችን ውል ያለብንን ሀሳብ ነፍሳችን ለመከወን ከተቻኮለች ብዙ ጊዜ ሸር ነው ሚሆነው። ውል ያለብንን ሀሳብ ለመስራት ከተሰናፋችና ወደ ኋላ ካለች ብዙዉን ጊዜ ኸይር ነው ሚሆነው።

ልባችን ላይ የሆነ ሀሳብ ውል የሚልብን ከሆነና ኸይር ይሁን ሸር መለየት ከቻልን ቀጣዩ እርምጃችን ከሸይጣን ፣ ከነፍስያ ነው አልያም አላህ ሱወ ኢስቲድራጅ አድርጎብን ነው የሚለውን መለየት ያስፈልጋል።

በልቦናችን ላይ ውል ያለው መትፎ ሀሳብ በእስቲግፋር ፣ በተዐውዝና በዚክር የሚወገድ ከሆነ ከሸይጣን ነው።
በዚክር አልወገድም ያለ እንደሁ?
ለምሳሌ አንድ ሰው ልጅ ሲወለድለት ዘመዶቹ መጥተው አልዘየሩት። ታድያ እነሱም ሲወልዱ ነፍስያው " እኔ ጋር ሳይመጡማ እኔም በፍፁም አልሄድም " ብላ ድርቅ ትላለች። ዝምድና መቁረጥ ከትላልቅ ወንጀሎች መሀል ነው። ታድያ ይህን ስሜት ምንም ያህል ዚክር ቢከረርበት ሊወገድ አይችልም። ምክንያቱም ኸዋጢሩ የመጣው ከሸይጣን ሳይሆነ ከነፍስያ ነውና።
የነፍስን የሸር ኸዋጢር ለማከም ሙጃሀዳ ማድረግ ይኖርብናል። ነፍስን መታገል። የሆነን ጥፋት ስታጠፋ " ነገ ትፆምያለሽ ፣ ለይሉንም ትቆምያለሽ.." እያልን ዳግም እንዳታጠፋ በኢባዳ መቅጣት። እንዲህ ስናደርግ ለተወሰኑ ቀናት ትነጫነጭ ይሆናል እንጂ መስመር ይዛ የአላህ አምር ላይ ቀጥ ማለቷ አይቀርም።

ሶስተኛው ወንጀል ሰርተን ምንም አይነት ፀፀትና ሀዘን ሳይሰማን ሲቀር ፣ ይልቅ ስለ ሰራነው ጥፋት እንደ ጀብድ ስናወራና ከተውባ ስንሰናፋ   አላህ ሱወ ከባድ አያያዝን ሊይዘን በሌላ የጥፋት በር ይፈትነናል። ወንጀል ላይ ወንጀል እንድንከማምር ልባችን ይወተውተናል።
እንዲህ አይነት ሀል ሲገጥመን ሱነተ ተውባ ሁለት ረከዐን ሰግደን ልባችንን እያስተናነስንና ራሳችንን እየወቀስን ከራህማኑ ጋር በማውጋት ልባችን ይታከማል።

. . .ወደ ልብ 

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

03 Feb, 16:18


የልብ ጉዞ~5

በሰዎች ዘንድ አምሮ ለመታየት ውጫዊ ገፅታችንን በተለያዩ ነገራቶች እንደምናስጌጥ እሙን ነው።
አላሁ ሱብሀነሁ ወተዐላ ደግሞ ወደ ውጫዊ ገፅታችንም ሆነ ቁመናችን አይመለክትም። የአላህ እይታ ወደ ልባችን ነው። ታድያ ለሰዎች ምልከታ ብለን ውጫዊ ገፅታችን ላይ እንደምንጠበበው አላህ የሚያየውን ልብንስ ለማስጌጥ ለምን አንጥርም?

ልብ ከተስተካከለች ሙሉ ሀላችን ይስተካከላል። ሙነወራ የሆነ ልብ ባለቤት ሰርክ ወደ አላህ ይናፍቃል። አላህን ያፈቅራል። ስለ አላህ ፍቅር ያነባል። ልብ ውስጥ የሸሸገው ፍቅርና ናፍቆትን በእምባው ይገልፃል።

ይህች ልብ በሶስት የስሜት ህዋሳቶቻችን ምክንያት ፅልመት ትሞላለች። ብርሀኗ ይከስማል። እነዚህ ሶስቱ የስሜት ህዋሳቶቻችን አይን ፣ ምላስና ጆሮ ናቸው።

" #አይን የተረገመው ሸይጣን የተመረዘ ቀስት ነው። "
አይናችን የሚያየውን ልባችን ላይ ይታተማልን አይናችን ኑራኒይ ወደሆኑ ነገራቶች  . . ወደ ቁርዐን ፣ ወደ ሳሊሆች ፣ ወደ ፍጥረተ አለሙ በተፈኩር ፣ ወደ ወላጅና ጓደኞች በሙሀባ የሚመለከት ከሆነ ልብ በብርሀን ይሞላል።

አይን ሶስት ነገራቶችን ስታይ ልብ  ፅልመት መልበስ ይጀምራል።
የመጀመሪያው የሸህዋ እይታ ነው። ነፍስ ምትሻው ሀራም ወደሆነ እይታ መመልከት። አጅነብይን ሴት ማየት አንዱ ለልብ ፅልመት መንስኤ ነው።
ሁለተኛው ዱንያን በማላቅ እይታ ማየት። እጅግ በማዳነቅና በማተለቅ መመልከት ከአይን የሚመጣ ለልብ ፅልመት ሰበብ ውስጥ ኣንዱ ነው።
የመጨረሻው ሌላን ሰው በንቀትና በማሳነስ እይታ መመልከት። ሰውዬውን በገንዘብ አልያም በስልጣን ወይ በዘሩ አሳንሶ መመልከት!
በኢልምም ቢሆን ማንንም አሳንሰን እንዳንመለከት የሚያዘን ዲን ነው ያለን።
ኢልም እኮ ወይ ላንተ አልያም ባንተ ላይ ሁጃ ብቻ ነው። ሀብትም ከሆነ ከሀላል ከስበህ በሀላሉ ካዋልከው አላህ ዘንድ ሂሳብ ሲጠብቅህ ከዛ ውጪ ቅጣት ነው።

በበኒ ዒስራዒል ጊዜ አላህን ለ500 አመታት የተገዛ አቢድ ነበር። ለዚህ ሰው ፀሀይ በሆነበት ስፍራ አንጣላው ምትሄድ ደመናም ነበረችው። ታድያ አንዴ መንገድ ላይ በበኑ ኢስራኢል ዘንድ እጅግ ወንጀለኛ ከሆነ ሰው ፊት ለፊት ይገጣጠማሉ። ሲተያዩ ሁለቱም ፊታቸውም አዙረው በመጡበት ይመለሳሉ።
አቢዱን ሰው ተከትላ የመጣችው ደመና ግን ፋሲቁን ሰው ተከትላ ሄደች። ምክንያቱም ወንጀለኛው ሰው አቢዱን ሲያይ ራሱን አሳንሶ እንዲህ ያለን የአላህን ባሪያ ለማየት ምገባ አይደለሁም በማለት ነበር ያፈገፈገው። አቢዱ ሰው ግን ለአመታት አላህን ያመፀን ሰውማ አልመለከተውም። በማለት ተጠይፎና አሳንሶት ነበር የዞረው። ሁለቱም በአይኖቻቸው ቢተያዩም የአንዱ እይታ ኑራኒይ ሲሆን የሌላኛው የፅልመት እይታ ነበር።
ኢባዳን በጨመርን ቁጥር ኢባዳችን ይበልጥ መፍራትና ራስን ማስተናነስን ሊጨምርልን ይገባል እንጂ ቅንጣት ኩራት ሊጠጋን አይገባም።

ሌላኛው ለልብ ፅልመት በር የሆነው ምላስ ነው።
ምላስ ደጋግሞ የሚከርረውን ነገር ማወቅ ልባችን ፅልመት አልያም ኑር እንዳንዣበበት ለማወቅ ይረዳናል። ንግግራችን ከሀሜት ፣ ውሸት ፣ ስድብ ፣ ሰውን ማነወር እና ዱንያዊ ነገራቶች ላይ ብቻ የተንጠለጠለ ከሆነ ልባችን ስር ድቅድቅን እየሸቀሸቅን ነው።
ምላሳችንን አላህን በማስታወስ ካረጠብን ፣ በቁርዐን ዜማ ካላወስን ፣ በመልካም ለማዘዝና ከመጥፎ ለመከልከል ከዘረጋናት፣ ሰርክ ስለ አላህና መልዕክተኛው ምንዘክር ከሆነ ልባችን በኑር ይሞላል።

የመጨረሻው በር ደግሞ ጆሮዎችን ነው። ሀሜት ፣ ውሸት ፣ ስድብ ፣ ዘፈንና ዱንያዊ የሆነ ነገራቶችን ምናዳምጥ ከሆነ ፅልመት ድሩን ቀልብ ውስጥ ያደራል። በተቀራኒው ቁርዐን ፣ ዚክር ፣ ሀዲስ ፣ የደጋጎች ታሪክና ኢማንን የሚጨምሩ አኼራዊ ጉዳዮችን አዘውትረን ምንሰማ ከሆነ የልባችን ኑር ያብባል።

ከአይን ጆሮና ምላስ በተጨማሪ ለልብ ፅልመት ሰበብ የሚሆኑት. . .

እንቀጥላለን . . .

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

03 Feb, 12:02


አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ!

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

30 Jan, 06:50


የልብ ጉዞ~3
:
ልባችን ወደ አላህ መጓዝ የሻ እንደሁ ያንን ፍላጎትና ተነሳችነትን ለመጠበቅ መጣር አለብን።
ይህንን ለማድረግ ከመጥፎ አቀማማጮች መራቅ ፣ መልካም ወዳጆችን ማብዛትና የሸይጣንን ጉትጎታ መቃረን እንደሚረዳን አሊሞች ያስቀምጣሉ።

እነኚህ ተግባራት ሂማችን እንዲዘልቅ ያደርጉናል። የአላህ ሙሪድ ለመሆን መንገድ የገባን ሰው አላህ ያግዘዋል። ወደ አላህ ለመጓዝ ልክነትን አንጠብቅ። ባላንበት ሀለት እየዳህንም ፣ እያንካሳን ፣ እየተራመድንም ይሁን እየሮጥን ወደ አላህ መጓዝ እንጀምር።

ልባችን ላይ ወደ አላህ ለሚደረገው ጉዞ የሚሆነንን ሂማ እያጠናከርን ወደ ተውባ መቅጣጨት ይኖርብናል። የጉዞዋችን የመጀመሪያው እርምጃ ከአል-ተዋብ ደጅ ተውበትን መማፀን ነው።  አመፅና ጥፋት በር ነው ሁላችንም የገባንበት። ባህር ነው ሁላችንም የዋኘንበት። አላህ ከጠበቃቸው በስተቀር ። ከአላህ ጋር የሚኖረንን ግኑኝነት ለማደስ በተውባ በር መዝለቅ ይኖርብናል።


ተውባ ሶስት አይነት ነገራቶችን አጠቃሎ የያዘ ነው።
ኢልም ፣ ሀል እና ፊዕልን ያካተተ እንደሆነ ተውባው የፀና ይሆናል።

ኢልም( እውቀት) ሲባል ባርነታችንን ማወቅ። በቅርቢቷ ሞት እጅግ አጭር ሚባል ድምዳሜ እንዳለን ማስታወስ። አላህ ፊት ለሂሳብ ያለ አስተርጓሚ እንደምንቆም ማወቅ።

ከፊቱ ቆመን. . .
ባሪያ ሆይ እንዲህ እንዲህ ቀንን ታስታውሳለህን? በሮችን ዘጋግተህ ከሶዎች እይታ ተሸሽገህ ክልከላዬን ስትዳፈር? ሰዎች እንዳያዩህ እፍረት ይዞህ ከኔ ግን ሀያዕ አልያዘህም? ባሪያዬ ሆይ ለምን ከሁሉ ፍጥረታት  እኔን ደካማ ተመልካች አደረግከኝ?
ባሪያዬ ሆይ በፀጋዎቼ ኮትኩቼ አሳድጌህ ለፀጋው በቂን ምስጋናን እንኳን ሳታደርስ ክልከላዬ ላይ ተዘፈቅ።
ባሪያዬ ሆይ  . . . .

እያለ ስላከናወናቸው እያንዳንዱ ተግባር እንደምንተሳሰብ ማወቅ።
ያከናወናቸው ተግባራትና ንግግር ሁሉ በሁለቱ ምንከውነውን ለመፃፍ ሙወከል በተደረጉ መላዒካዎች እንደሚከተብ ማወቅ።

አንድ ሀበሻዊ የሆነ ሰው ወደ አንድ ደግ ሰው ይሄድና
" ያ ሸይኽ የሰራሁት ወንጀል አለ አላህ ይምረኛልን? " ሲል ጠየቃቸው።
" አዎን እውነተኛ ተውበት ካደረግክ ይምርልሀል " አሉት።
ደስታው ፊቱ ላይ እየተነበበ በፈገግታ ተራመደ። ቆም ብሎ ወደ ሸይኹ ተመለሰና
" ያ ሸይኽ ወንጀሉን ስሰራ እያየኝ ነበርን? " ብሎ ጠየቃቸው። " አዎን! " ብለው ሲመልሱለት በድንጋጤ ጩሆ ወደቀ። ከወደቀበትም ዳግም ላይነሳ በዛው አሸለበ።

የሀቂቃ አላህ አላህነቱን ካወቅን ልባችን ላይ የሚኖረው አዘማ ወንጀል እንዳንሰራ ብቻ ሳይሆን መስራትንም እንዳናስብ ያደርገናል።

በአላህ እይታና እውቀት ውስጥ እንደሆንን የሀቂቃ ስናውቅ ላጠፋነው ጥፋት ፀፀት ይሰማናል።
ያለንበት አሁናዊ ሀል ( ሁነታችንን ) ይገለጥልናል። ልባችን ስብር ይላል። እምባ የአይኖቻችንን ግድብ ይሞላዋል። ፀፀት ይገርፈናል።

ከበፊት ሰለፎች መካከል ፦
" ዋ ጥፋቴ ! ብትምረኝ እንኳን " እያሉ ሚያለቅሱ ነበሩ።
አላህዬ ቢምረኝም እንኳን ሊታመፅ የሚገባ ጌታ አይደለም እያሉ ሰርክ የሚያነቡ ነበሩ ።

ይህ ፀፀት ወደ #ፊዕል ይቀየራል። ተግባር ላይ ሲውል ፅኑ ውሳኔን ወስነን ዳግም ወደ ማዕሲያው እንዳንመለስ ና ሙሉ ለሙሉ ከጨለማው ክብባት ወጥተን ወደ ብርሀናማው አለም ጉዞ ለማድረግ ቁርጠኛ እንሆናለን።

ከልብ ጉዞ የመጀመሪያው እርምጃ . . .

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

29 Jan, 04:12


• ሁሉም ነፍስ ሞትን ቀማሽ ናት •

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

28 Jan, 18:49


የልብ ጉዞ~2
:
የልብ ጉዞ ለማድረግ ሂማ ያስፈልጋል። ከገፍላው ተነሳሽነት እንዲኖር የሚያደርገው አላህ (ሱወ) በልብ ላይ የጣለው ቀስቃሽ ስሜት ነው። ይህ አንቂ ስሜት
"ባዒስ" ይሰኛል።

ለአንድ የሰርግ ድግስ የጥሪ ወረቀት የደረሰው ሰው በቀጠሮ ሰዐት ለመሄድ ይነሳል። ድግሱን ይታደማል።
ያን ድግስ እንዲታደም ተነሳሽነት እንዲኖረው ያደረገው የጥሪዋ ወረቀት ናት።

የጥሪዋ ወረቀት እንደ "ባዒስ" ናት ጥሪው ከደረሰን ቡኋላ ለመሄድ የሚኖረን ተነሳሽነትና ለመጓዝ መሰናዳታችን ደግሞ ሂማችን ነው።

ለልብ ጉዞ ስንሰናዳ ሂማ እንዲኖረን ይህ "ባዒስ" እጅግ ያስፈልገናል።  የተነሳሽነትና የመልካም ጉጉት ስሜታችን እንዲያብብ የሚያደርገንን  " ባዒስ " በሶስት አይነት መልኩ ልናገኘው እንደምንችል አሊሞች ይናገራሉ።

አንደኛው በ #ተርሂብ ሲሆን የአላህን ቅጣት ፈርተን ካለንበት ጥፋት እንድንታቀብና በኢባዳ ላይ እንድንቻኮል ያደርገናል።

እንደ ምሳሌ አንድ ሰራተኛ በቢሮ ውስጥ በተደጋጋሚ እያረፈደ በመምጣቱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውና " ነገ ካረፈድክ ከስራ ትባረራለህ" ቢባል። ንጋት ላይ ማልዶ ቢነሳና ነፍሱ እንቅልፍ ቢያምራት እሺታውን ይቸራታል? የነፍሱን ፍላጎት ከተከተለ የሚደርስበትን ቅጣት ያውቀዋልና ነፍስያውን ተቃርኖ ከቅጣት ይድናል።

ሌላኛው መንገድ ደግሞ #ተርጊብ ይሰኛል። አላሁ (ሱወ) ለአማኞች ያዘጋጀውን ምንዳን ስናደምጥ። የጀነት ውስጥ ፀጋ. . ወንዞቹ ፣ ፍራፍሬዎቹ ፣ ሁረል ዐይኖቹ . . .የተለየዩ የማይከስሙ የአኼራ ፀጋዎችን ስናስተውል ለኢባዳ ሂማ እንዲኖረን የሚያደርገንን ባዒስ እናገኘዋለን።

ምሳሌ . . .አባት ለልጁ ይህን አመት አንደኛ ከወጣህ ብስክሌት እገዛልሀለሁ ቢለው ያ ልጅ ማጥናት ሲሰለቸው ወይም ጫወታ ሲያምረው ከጥናቱ ጀርባ የሚያገኘውን ስጦታ እያየ በነፍሱ ሳይሸነገል ሽልማቱን ለማግኘት ይጥራል።

አላህ (ሱወ) ዘንድ ስላለው ዘውታሪ ኒዕማ መስማትና ማሰብ በኢባዳችን እንዳንሰናፋና በነፍስያ መዳፍ እንዳንጨፈለቅ የሚያደርገንን ሂማ እንዲኖረን ይረዳናል።

ሶስተኛው. . . #ሸውቅ ነው። አላህን ሱወ መናፈቅ . . ማፍቀር። የዋለልንን ፀጋ በማስተንተን ፣ ፍጥረተ ዐለሙን በማጤን ፣ በተለያዩ የቁርዐን አያዎችና አሀዲሶች ውስጥ የርሱን ፍቅር መፈለግ።
የራስን ብዙ ጥፋት . . .የርሱን ሰፊ እዝነት ማሰብ።

በአንድ ጦርነት ላይ አንዲት እናት ከልጇ ጋር ትጠፋፋለች። በትርምሱ መሀል ያገኘችውን ህፃን እቅፍ አድርጋ ከደረቷ እያስጠጋች ልጇ መሆኑን ታረጋግጣለች። ካልሆነ አስቀምጣው ፍለጋዋን ትቀጥላለች። በዚህ መሀል ልጅና እናት ይገጣጠማሉ። እናት ተንሰፍስፋ ልጇን እቅፏ ውስጥ ሸሸገችው።
ይህንን ትዕይንት እየተመለከቱ የነበሩ ሰሀባዎች ልባቸው ተነክቶ አለቀሱ።
በዚህ መሀል ረሱላችን አለይሂ ሰላቱ ወሰላም ምን እንደሚያስለቅሳቸው ሲጠይቋቸው የልጅዬውና የእናቱ ሁነት እንደሆነ ይናገራሉ።
ረሱላንችንም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም " ይህች ሴት ልጇን እሳት ውስጥ ትጥላለች ብላችሁ ታስባላችሁን? " ብለው ጠየቋቸው።  በፍፁም  አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሲሉ መለሱ።
ረሱለሏህም " አላህ ይህች ሴት ለልጇ ከምታዝነው በላይ ለእናንተ አዛኝ ነው። " ሲሉ ተናገሩ።

ይህን አዛኝ ጌታ አዛኝነቱን ማወቅ። ችሮታውን ፣ ፍቅሩን ፣ መሀሪነቱን ፣ ሰታሪነቱን ፣ ገፋርነቱን ፣ ይቅር ባይነቱ ከልብ ማሰብ ወደ አላህ ለምናደርገው ጉዞ ሂማ እንዲኖረን የሚያደርገውን " ባዒስ"ን ይቀሰቅሳል።

ሳሊሆችን መቀመጥም ለኸያራት ሂማ እንዲኖረን ያደርገናል። ከቀደምት ሳሊሆች
" ሙሀመድ ኢብኑ ዋሲዕን ስመለከት ለወር ያህል ኢባዳ እንድሰራ በሚያስችለኝ ሂማ እሞላለሁ። " የሚል ነበር።


እንደው ስናጠቃልለው . . .
በማዕሲያ የተጠመዱ ሰዎች የሚደርስባቸውን ቅጣት በማስታወስ አልያም ለሙተቆች የተዘጋጀውን መስተንግዶን ስናደምጥ ወይም አላህን ሱወ ስንናፍቅና ከደጋጎች ጋር ስንቀማመጥ ለልብ ጉዞ የሚሆነንን ሂማ እናገኛለን።
____
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

27 Jan, 16:11


የልብ_ጉዞ ~1
:
ነፍስ በክጃሎቶቿ ተሳስራ የሩህ ኑርን አክስማ እንስሳዊ መገለጫዎቿን በምታጎላበት ጊዜ  ወደ ቀድሞው ማንነቷ ትመለስ ዘንድ የሽሽት ጉዞ ያስፈልገናል። መሻቶቿ ገደብ የሌለው ነውና ፍላጎቷን ሙሉ ለሙሉ ወደ አላህ ውዴታ ለማቅጣጨት መጣር አለብን።

ነፍስ በእያንዳንዱ እንቅስቃሴዋ ውስጥ የአላህ ውዴታን መሻት እንድትችል መጣር ያስፈልገናል። የነፍስያን እኩይ ክጃሎትን ኩታ አውልቀን የሙሀባን ኑር ወደማጥለቅ . .

ሀቢባችን ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም " በሰውነት ውስጥ አንዲት ቁራጭ ስጋ አለች። እርሷ ከተስተካከለች ሌሎች አካላቶች ይስተካከሉ። እርሷ ከተበላሸች ሌሎች አካላቶችም ይበላሻሉ። አዋጅ! እርሷ ልብ ናት።" ብለውናል።
የቀልብ መበላሸት የመላ ተግባራችንን ክስረት አመላካች ነው። መስተካከሏ ደግሞ የመድህናችን በር ነው። 

ብዙ ጊዜ አንድ ሰው በሚወደው ሰው ላይ በግልፅ የሚታየውን ጥፋት አይመለከትም. . .ለዛም ነው በራሳችን ላይ ያለውን እድፍ ማየት ሚሳነን።
እይታችን እንዲጠራ ራሳችንን በጠራ መነፅር መመልከት እንድንችል ልብ መስተካከል አለባት።

አላህን መፍራት፣ ለርሱ ልብን ማስተናነስ ወደርሱም መዋደቅ ፣ ስራን አጥርቶ ለርሱ መስራት፣ ራስን በጥፋተኝነት መውቀስ. .ሁሉም አላህ ዘንድ የሚታወቁ የቀልብ አምልኮዎች ናቸው። እነኚህ የልብ አምልኮዎችን ለማከናወን ልብ ከእዩልኝ ልትጠራ፣ ከኩራትና ከመኮፈስ ስሜት ልትፀዳ፣ ከንፍቅና ፣ ከሂስድና መሰል በሽታዎች ሁር ልትሆን ይገባል።

አር-ራፊዒ በእግር ከሚደረግ ጉዞ በልብ የሚደረገው ጉዞ ይበልጥ እንደሚፈጥን ሲመሰክሩ እንዲህ ይላሉ
" ወደ ልብ የሚደረግ አጭር ርቀት ወደ ሰማይ ረጅም ርቀትን ይዘልቃል።"

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

26 Jan, 19:10


:اللهم صل على صاحب التاج والمعراج سيدنا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليما، وكن بنا وبوالدينا وبمشايخنا وبالمؤمنين رؤفا رحيما.

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

26 Jan, 13:54


የልባችን ላይ ዝገት እንዲፋቅ : የነፍስ እስትንፋሳችን እንዲታደስ ልባዊ ጉዞዋችንን ሰርክ ማደስ አለብን ። እየመጣ ላለው ታላቅ እንግዳ : የነፍስ ተሀድሶ ለማድረግ በሚረዳን ፅሁፍ ዳግም እንገናኛለን።

#የልብ_ጉዞ ከአንዳንድ ማስተካከያዎች ጋር ዳግም ምንገናኝበት ፅሁፍ ይሆናል።

አላሀመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ💚

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

26 Jan, 12:04


#በኢስራእ_ወልሚዕራጅ

^
^
^
ከፍ ... እንበል ^^^

ዓለማት ትርጉሙ ብዙና ጥልቅ ነው። የአልፋቲሓ ምዕራፍ ሲጀምር ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ ይገባ ብሎ ይጀምራል። የምናቃቸው ዓለማት ውስን ናቸው። የማናቃቸው በቁጥር አይገለጹም ቃልም ስለሌለን ዝም ብለን " አልሐምዱ ሊላሂ ረቢል ዓለሚን" እንላለን።

ታዲያ ዓለማቱ ኹሉ በአላህ አምር (ትዕዛዝ) ሥር ማለትም፦ ዐለማቱ ኹን (ኹን) (كن فيكون) በሚለው ቃሉ ስር ነው ያለው ማለት ነው። ዐቅልም የተለመደ ጥያቄውን ይጠይቃል፣ አስገራሚ ነገሮችን መቀበል እያቃተው ጥያቄውን ይቀጥላል።

የኢስራእ ጉዞ ከሰው ልጅ አዕምሮ በላይ ነዋ፤ ሰይድናችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የተኙበት ፍራሽ ሙቀት ሳይበርድ ነዋ ያን ኹሉ ዓለም የመጡት! ለዚህ ነው ይህን ክስተት ለመረዳት መጀመሪያ አላህን ማጥራት የሚያስፈልገው። ከምን? አላህ ነገሮች ኹሉ ማድረግ እንደሚችል ከማመን ጋር ከማይገባ ጥርጣሬ ኹሉ እንድንወገድ ልብን መጠበቅ አስፈላጊነት ያጸናል።

ቁርኣኑ በአልኢስራእ ምእራፍ መጀመሪያ እንዲህ አለ

“ያ ባሪያውን ከተከበረው መስጊድ ወደዚያ ዙሪያውን ወደ ባረክነው ወደ ሩቁ መስጊድ በሌሊት ውስጥ ያስኼደው (ጌታ) ጥራት ይገባው፡፡ ከተዓምራቶቻችን ልናሳየው (አስኼድነው)፡፡ እነሆ እርሱ (አላህ) ሰሚው ተመልካቺው ነው፡፡”

ምዕራፉ የጀመረው "ሱብሐነላህ" ብሎ ነው። እንዲህ አይነት ተዓምራት የሚገባው ሰው ደግሚ አዋቂ ኾነ ዝነኛ ወይም ሌላ ማዕረግ አልተቀመጠም። ማዕረጉን በግልጽ ቁርኣን ላይ ሲቀመጥ "ባሪያ" መኾን እንዳለበት ነው የተቀመጠው።

ኢስራእና ሚዕራጅ ራሱ እንዲገባን ባሪያ መኾን አለብን።

ባርያው ያድርገና


©Best_Kerim

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

24 Jan, 19:34


"  በባሮቼ ላይ ሁለት ፍርሀትን አልሰበስብም። በዱንያ ላይ የፈራኝ አኼራ ላይ ሰላም አደርገዋለሁ። "
:
#አላሁ💚

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

24 Jan, 19:34


• በአላህ ፍራቻ ማልቀስ...! •

" የታለበ ወተት ወደ ጓቱ እስካልተመለሰ ድረስ በአሏህ ፍራቻ ያነባችም አይን ወደ እሳት አትገባም። "ሀቢበሏህ

ሰይዲና ኡመር (ረዐ) በአላህ ፍራቻ አብዝተው ያለቅሱ ነበር። "ምነው እናቴ ወልዳኝ ባልነበር!" እያሉ ያነቡ ነበር። ከለቅሶዋቸው ብዛት ጥቋቁር የእምባ መስመሮች በፊታቸው ላይ ይታይ ነበር።
:
የቂያማ ዕለት አንድ ወንጀለኛ ሰው መልካም ስራው አንሶ ወደ ጀሀነም ይነዳል። በዚህ መሀል የአይኑ ሽፋሽፍት ላይ ያለች ፀጉር አማላጅ ሆና ትቆምለታለች። " ጌታዬ ሆይ! መልዕክተኛህ በአላህ ፍራቻ ያለቀሰች አይን ጀሀነም አትገባም ብሎን ሳለ እንዴት በእምባው እርጥበት የራስኩት እኔ እሳትን እገባለሁ። በፍራቻህ በረገፈችው እምባ ረጥብያለሁ። " በአንዷ ፀጉር በረካ አላህ በምህረቱ ለቅጣት የታጨውን ሰው ወደ ዳሩ ሰላም እንዲሄድ ያደረገዋል። ከጀነት ሰዎችም ይሆናል።

ሀቢባችንም ﷺ " አላህ ሆይ! ለአይኖቼ በፍራቻህ ማልቀስን ረዝቃቸው። እምባ የማይኖርበት ቀን ከመምጣቱ በፊት። " ይሉ ነበር።
..
እምባ ማጣት የቀልብ መድረቅ ምልክትም ነው።
ስለ ፍራቻው ፣ ስለ ፍቅሩ ስለ እርሱ ብለን የምናነባውን እምባ ይርዝቀን። አሚን!!
:
@Ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

21 Jan, 11:46


ኢማም አል-ቁሸይሪ (ረሂ) እንዲህ ይላሉ፦
ለአንድ ሸይኽ ሁለት ተማሪዎች ነበሩት። እነኚህ ሁለት ተማሪዎች በአንድ ጉዳይ ላይ ተለያዩና ወደ ሸይኻቸው ለመዳኘት ሄዱ።
አንደኛው " መተኛት/እንቅልፍ ከንቃት ይሻላል። ምክንያቱም ሰውዬው በተኛበት አሏህን አያምፅምና" ብሎ ተናገረ። ሌላኛው ደግሞ " መንቃት ከመተኛት የተሻለ ነው። ምክንያቱም በንቃት ወቅት ሰውዬው አሏህን ያስታውሳልና።" ብሎ ሀሳቡን አቀረበ።
ሸይኹ ወደ መጀመሪያው ተማሪ ዞር አሉና። " መተኛትን ከመንቃት ይሻላል ያልክ እንደሆነ። ሞትህ ላንተ ከመኖርህ የተሻለ ነው።"
ወደ ሁለተኛው ተመለሱና " መንቃት ከእንቅልፍ የተሻለ ነው ያልከው። መኖርህ ከሞትህ የተሻለ ነው።"

@Ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

21 Jan, 11:45


<ዱንያ የአኺራ እርሻ ናት!>
:
••[ በግልም ሆነ በቡድን የምናደርጋቸው እንቅስቃሴዎችና ጥረቶች በዱንያ ውስጥ አንዳችን ሌላችንን በልጦ ለመገኘት የታለመ ከሆነ የአኺራ ምንዳ ያመልጠናል። ውድድራችን በአኺራ ላይ በሚገኝ ምንዳ እና ለአላህ በሚኖረን ቅርበት ላይ ከፍተኛውን ስፍራ ለማግኘት ከሆነ ግን የታደልን ሰዎች ነን። በአኺራ ላይ ምንዳችንን ከፍ ለማድረግ ከምንጥርባቸው መንገዶች አንዱ ባለን ሀይል ተጠቅመን የሙስሊሙን ህዝብ ዱንያ ለማሳመር መትጋት ነው!
በዱንያው ውስጥ የሌሎች ተላላኪና ከሌሎች ጠባቂ የሆነ ህዝብ ከአኺራው በፊት ዱንያውንም የከሰረ ህዝብ ነው! ]••

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

21 Jan, 11:42


•[ በአላህ ይሁንብኝ በሁኔታዎች መስተካከልና በነፍስህ እርጋታ ትደነቃለህ. . .በድቅድቅ ለሊት ውስጥ ተሸሽገህ ባደረግከው ዱዐ ሰበብ! ]•

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

20 Jan, 16:23


ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]• pinned Deleted message

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

18 Jan, 14:25


| አንቱን ካ'የሁ ወድያ ፡ ብሞትም ግድ የለኝ! |

ሀቢቢ ያ ረሱለላህ❤️‍🔥

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

18 Jan, 14:18


«የሰው ልጅ በህይወት ሲኖር ሥራውን የሚሰራ ህላዌ [ዛት] ነው። ህይወት ሲያበቃ ደግሞ ስራው እርሱን ዘልዐለማዊ የሚያደርግ ህላዌ ይሆናል። መልካም ከሰራ መልካም ሆኖ ለዝንተዐለም ይዘልቃል። ክፉ ከሰራም በክፋቱ ዝንተዐለም ይዘወትራል። ሞት ማለት ሩሕ ከሥራዋ የምትወለድበት ክስተት ይመስላል። ሩሕ ሁለቴ ትወለዳለች። አንዴ ወዲህ ስትመጣ፤ ሌላም ወደመጣችበት ስትሄድ።»
ሙስጠፋ ሳዲቅ አር‐ራፊዒይ፥ ወሕዩል‐ቀለም

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

18 Jan, 14:18


💗 ያ አሏህ

ያንተ መሆን መታደል ነው!

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

18 Jan, 14:01


| ከሰዎችም አሉ ንፁህ ማር ብናጠጣቸው ራሱ በእኛ ላይ ጥላቻን እንጂ የማይጨምሩ፤ ከሰዎችም ውስጥ አሉ አካላቸውን ብንቆራርጠው እንኳ በእኛ ላይ ፍቅርን እንጂ የማይጨምሩ! |
:
ኢማም አሊ (ከረመሏሁ ወጅሀህ)

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

18 Jan, 14:00


| በሀያታቸው በረካ የዘመኑን ደብዛዛ ገፅ በብርሀን እልፍኝ ያስጌጡ፡ ያላዋቂነትን ድቅድቅ በዕውቀታቸው ብርሀን የረቱ፡ በኑረታቸው ከሠበሰቡት የዕውቀት ካዝና ሳይሰስቱ የሚመፀውቱ...ትውልድን የመግራት፡ ኡማውን በምግባርና በዕውቀት ለማነፅ ሌት ተቀን የሚታትሩ..ቸሮች። የድፍርሱን አለም እውነተኛ ገፅታን ለማሳየት የሚጥሩ። ወደ ብርሀን ጠቋሚ ሆነው የተሰየሙ...የብርሀን ክምሮች። ተርታው ህዝብ ቀድራቸውን በመሳት..ወደ ብርሀን ለመጠቆም ከቀሰሩት ጣት ላይ ነውርን እያሰሰ..ክብራቸውን ለማጉደል የሚጥር..እውነታው የራሱ ቢሆንም ሚጎድለው..ሆኖም ፅኑ ታጋሾ።  ከእውነትና ከፍትህ ጎን ሁሌም ሚሰየሙ። ዛታቸው አንድ ቢሆንም ግብራቸው የእልፎችን ሽንቁር የሸፈነ። የዘመን ፈርጦች...! በአደብ የዳበሩ..በእውቀት፣ በሙሀባና ተቅዋ የተማመሩ! |

#ባሮች_አሉት!
:
( አብዱ ሩሚ )
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

18 Jan, 13:54


አብረውን እያሉ ልካቸውን ያላወቅንላቸው፡ በኑረታቸው ደፍራሳው ደስታችን ሳናውቀው የሚረጋ። በድቅድቅ መሀል ፋኖሳቸውን ይዘው ከጨለማው ያሻገሩን። ስብርብር ባልንበት ወቅት አፋፍሰው ያነሱን። ሀዘናችንን ያስረሱን። ደስታን ያስታቀፉን። መዐበላማው ህይወት ላይ ነፍስ አድን ጨልባ ሆነው የተከሰቱልን። ከመስጠም ያስጣሉን።
:
ሩህ ላለው ፍጡር ሁሉ ሩህሩህ የሆኑ፡:የአዛኝ ልብ ባለቤቶች። የጌታቸውን ውዴታ በመሻት ኸልቁን ከልብ ሚያፈቅሩ። ለደካማው የድጋፍ እጃቸውን የሚለግሱ፡ ለትቢተኛውም ደግነታቸውን የማይነፍጉ። እንደ ወራጅ ወንዝ ለሁሉም በብዙ መልኩ መጠቃቀምያ ተደርገው የተኸለቁ። የራሳቸውን ጉዳይ ጥለው በሌሎች ሀጃ ላይ ሚብሰለሰሉ። በወንድም ጉዳይ ተጨንቀው ዳዓ ሚያደርጉ ፡ በደስታና ፌሽታው የቅርቡ አባሻሪ ሆነው ሚሰየሙ። በዘመን ሙግደት፡ በሀሲድ ብዛት ከመልካም ማይጎድሉ የሩህ ጓዶች። የደግነት ማዐዶች የሆኑ..
:
#ባሮች_አሉት!
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

07 Jan, 18:48


መቼስ..
ደቂቁ እኔ
ከእጥፋቴ ባልቀና
ጥፋቴ ለቃል ቢጠና
ውስጠቴ ቢሆንም ኦና ፡
መተስፈይ አልተው
መማፀን አልተው
ጌታዬ  አንተ ነህና ፡

እኔ እኔ ነኝ
እልፍ መሰበር ያላደከመኝ
አንተ አንተ ነህ
በሰፊ እዝነትህ
ውድህ አድርገኝ
እኔን ከነፍሴ ገላግለኝ፤

እንደ ነጭ እርግብ ክንፌን ላማታ
ከእኔነቴ ላ'ንተ ልፋታ ፡
ይሰማኝ ስጠራህ እፎይታ
ስማልኝ የነፍሴን ዋይታ ፡

•[ አብዱ ሩሚ ]•

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

07 Jan, 18:34


ልቤ ባ'ንቱ ፡ ከኔ ሸሸ ❤️‍🔥

አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ!❤️‍🔥

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

06 Jan, 20:38


https://vm.tiktok.com/ZMrunAVYv/
#Follow

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

05 Jan, 10:18


አንድ አሊም ተጠየቁ አንድ ሰው ተውበት ሲያደርግ ተውበቱ ተቀባይነት ያግኝ አያግኝ ይታወቃልን?
" ይህ እንኳን በእርግጠኝነት ሚታወቅ ነገር አይደለም። ነገር ግን ምልክቶች አሉት። ተውበቱ ተቀባይነት ሲኖረው ነፍሱ ከሰራው ሀጥያት መላቀቁ፣ ደጋጎችን መቀማመጡና ከመጥፎ ሰዎች መነጠሉ አንዱ ምልክት ነው። ለዱንያ ሚሰራት ትንሽ ስራ ስትበዛበት። ለአኼራ ሚሰራው ብዙ ስራው ሲያንስበት። ቀልቡ አላህ በደነገጋቸው ነገራቶች ላይ ሲተሳሰር። ሰዐቲቱን ከሚጠባበቁት ሲሆን። ሁሌም በሰራው ጥፋት ሲብሰለሰልና ፀፀት ሲሰማው ቅቡልነቱን ማወቅ ይቻለናል። "  በማለት መለሱ...!
:
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

05 Jan, 10:14


" ሰላትህ እንዴት ነበር?"

• "በምንም አይነት ሁኔታ ላይ ብሆን ፡ በቀን አምስት ጊዜ የልቤን የማወያየው ማንም እንደማሌለኝ ተገነዘብኩ፡
ባዝን፣ ብሰበር ፣ ብደክም፣ ብታመምም...ከአዛኙ እጅግ በጣም አዛኝ ከሆነው አሏህ በስተቀር። "•

#አሏህ
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

01 Jan, 17:24


አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ!
😭

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

31 Dec, 21:30


ያ አላህ❤️‍🩹

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

31 Dec, 20:47


ታላቁ ዓሊምና የአላህ ወዳጅ ሰዪዲ ሸይኽ ዐብዱል ቃድር አል ጀይላኒይ(قدس سره)በመጀመሪያው የረጀብ ወር ሌሊት ይህንን ዱዓ እንድናደርግ በእውቁ "አል ጙንያህ"ኪታባቸው ውስጥ ጠቅሰዋል፤ዱዓውን ከነ ትርጉሙ አስቀምጨዋለው:–
إِلهِي : تَعَرَّضَ لَكَ فِي هذه اللَّيْلِة المُتَعَرِّضُونَ ،وَقَصَدَكَ القاصِدُونَ ،وَأَمَّلَ فَضْلَكَ وَمَعْرُوفَكَ الطَّالِبُونَ ؛وَلَكَ فِي هذه اللَّيْلِة نَفَحاتٌ وَجَوائِزُ ،وَعَطايا وَمَواهِبُ ،تَمُنُّ بِها عَلى مَنْ تَشاءُ مِنْ عِبادِكَ ،وَتَمْنَعُها مِمَّنْ لَمْ تَسْبِقْ لَهُ العِنايَةُ مِنْكَ، وَها أَنا ذا عّبدُكَ الفَقِيرُ إِلَيْكَ، المُؤَمِّلُ فَضْلَكَ وَمَعْرُوفَكَ؛ فَإِنْ كُنْتَ يا مَوْلاي تَفَضَّلْتَ فِي هذِهِ اللَّيْلَةِ عَلى أَحَدٍ مِنْ خَلْقِكَ ،وَجُدْتَ عَلَيْهِ بِعائِدَةٍ مِنْ عَطْفِكَ ،فَصَلِّ عَلى سَيِّدِنَا مُحَمَّدٍ وآلِهِ وَصَحبِهِ، وَجُدْ عَلَيَّ بِطَوْلِكَ وَمَعْرُوفِكَ، يا رَبَّ العالَمينَ .
አላህ ሆይ! በዚህች ሌሊት ቀራቢዎች ወዳንተ ቀረቡ፣አሳቢዎችም አሰቡህ፣ፈላጊዎች ትሩፋትና መልካምህን ተስፋ አረጉ፣በዚህች ሌሊት ውስጥ እድያዎችና ሽልማቶች፣ልገሳዎችና ስጦታዎች አሉህ፤በነሱም ከባሪያዎችህ የፈለግከውን ባሪያ ትመነዳለህ፤ካንተ የሆነች እገዛ ካያልቀደመችለትም ሰው ትከለክላለህ፤ይሄው እኔ ወዳንተ ፈላጊ፣ችሮታህንና መልካምህን ከጃይ ባርያህ!
ረዳቴ ሆይ! በዚህች ሌሊት በአንዳች ፍጡርህ ላይ ችሮታህን ለግሰህ፣በእዝነትህ ውለታን ውለህ ከሆነ፣አንተ የአለማት ጌታ ሆይ  በሰዪዳችን በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ እዝነትህን አውርድ፤ከፀጋህና ከመልካምህ ለኔም ለግሰኝ"
_
© t.me/hamidabuhamid

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

30 Dec, 17:43


የሰዎች ልብ ውስጥ በይበልጥ የገዘፈው ነገር "ጌታ" ለመኾን የቀረበ ነው። ሰዎች ራሳቸውን ለማወቅ ካልታገሉ። የፈለገ ቢማሩ፣ የፈለገ ሐይማኖተኛ ቢኾኑ አንደበታቸውና ገጽታቸው እነርሱን አይገልጽም። ሰዎች በሌሎች ዘንድ የሚፈልጉትን የቅቡልነት ፍላጎት፣ ሌሎችን የመቆጣጠር ስሜት፣ ሁሉንም ነገር ይገባኛል የሚል ነፍሲያ ሐቅ ላይ እንዳሉ በማሳየት ይጋርድባቸዋል። ይህ በነፍሲያ የመታለል አባዜ አላህንም ጭምር መርሳትን ያለማምዳቸዋል።

ሰዎች መስጂዶችን ሞልተው፣ ልዩ አልባሳትን ለብሰው አሸብርቀውና ደምቀው መላእክት መስለው ሲታዩ በክፋት በኩል የሚያልፉም አይመስሉም። ግና ከነጫጭ ጀለቢያዎች ጀርባ ያለውን ሰውን የመጥላት፣ ሰው ላይ የማሴርን፣ ሰው ላይ የመመቅኘትን ወኔ ማን ይኾን ያለበሳቸው?!

ሸይጣን???

መስጂድ ገብተው፣ ሰግደው፣ አንዳንዴም ጾምው፣ ከዚህም አልፎ ዑምራና ሐጅ ተመላልሰው?!

ሸይጣን አይደለም ያስቸገረን በዋናነት ያስቸገረን የገዛ ነፍሲያችን ነው። የአምልኮ ግብ ሳይገባን መስጂዶችን አጨናነቅን፣ በሰለዋትና ዚክር የሚለዝበውን ማንነታችንን በሚድያ ዲን ቀየርን። ለልባችን የሚጠቅሙ ሙረቢዎችን (መምህራንን) ኋላ ቀር ብለን የሚያብረቀርቁ የቲክቶክና የሚድያ ሸይኾችን ተከተልን። ውጪያችን የሚያበራ ውስጣችን የጨለመ ማንነት ወረስን።

ፖለቲከኞች እየተቀደሱ መንፈሳዊ ግለሰቦችን በንቀት ከቦታቸው በውርደት እንዲገፈተሩ ተደረገ። በፍጥነትም የገፈቱ ቀማሽ ኾንን ዛሬ መንፈሳዊነት ርቆናል፣ ኪታብ ብንሰበስብ፣ ዕውቀት ብናከማች ኢጃዛ (ፈቃድ) ከሌለ ዘውቁ ከየት ይመጣል። ዛሬም አልረፈደም በመረጃ ብዛት ያከማቸነው ሐይማኖት በሕይወታችን ውስጥ እንዲሰራ ከፈለግን ለልብ የሚኾነንን ዑለማ እንፈልግ። ፊታችንን ወደ ሰለዋት፣ ዱዓ እና ዚክር እንመልስ። ከልባችን ውስጥ ከገቡ ጣኦቶች ንሰሐ እንግባ።

አላህ ያስረዳን

© Best Kerim🩵

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

29 Dec, 17:17


ወሃብ ኢብኑ ሙነቢህ እንዲህ ብለዋል፡- “ከንባቦቼ መረዳት እንደቻልኩ የሰው ልጅ ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው ድረስ ያለው እውቀት ሁሉ በአንድ ሆኖ ቢሰበሰብ ከነብዩ ﷺ እውቀት ጋር ሲወዳደር እንደ ነጠላ የአሸዋ ቅንጣት ብቻ ቢሆን ነው። "
(አሽ-ሺፋ)

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

29 Dec, 17:15


ቃል አያክመው የልቤን ህመም
አብሽር አያሽረው
ረግፏልና የነፍሴ ለምለም፡
እምቡጧ ሩሄ ጠውልጋ
ንጋቷ ከስሞ
ድቅድቅ አለም ውስጥ መሽጋ ፡
ተላምዳ ከፅልሙ አለም
ወድቃለች
ጠፍታለች
ጭላንጭል ብርሀኗ የለም ፡

ማንም መሆኗን እስክታውቅ
ምንምነቷ እስኪገባት
መንገድ ለጠፋት ብክነት ለበዛት ፡
ድኩሟ ነፍሴን
አንተው ወዳንተ አድርሳት፤

ኸልቅ ሲዘክር
ወዱድ እያለ ሲከርር ፡
..
ሌላው ጋር ብርሀን ወግጎ
እኔ ጋር ፅልመት ሲወጣ ፡
ከወደቅኩበት ዝቅታ
ምርኩዜ ሁነኝ ልወጣ ፡

መቼስ..
ደቂቁ እኔ
ከእጥፋቴ ባልቀና
ጥፋቴ ለቃል ቢጠና
ውስጠቴ ቢሆንም ኦና ፡
መተስፈይ አልተው
መማፀን አልተው
ጌታዬ አንተ ነህና ፡

እኔ እኔ ነኝ
እልፍ መሰበር ያላደከመኝ
አንተ አንተ ነህ
በሰፊ እዝነትህ
ውድህ አድርገኝ
እኔን ከነፍሴ ገላግለኝ፤

እንደ ነጭ እርግብ ክንፌን ላማታ
ከእኔነቴ ላ'ንተ ልፋታ ፡
ይሰማኝ ስጠራህ እፎይታ
ስማልኝ የነፍሴን ዋይታ ፡

ላግኝህና መኖር ልጀምር
ቅፅበት ዘመኔን
ልኑር ስምህን ስዘምር።
_
•[ አብዱ ሩሚ ]•

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

28 Dec, 19:40


ጌታህ እነዛ ፡ ደጃቸውን ጠንተህ ከሚመልሱህ ሰዎች በላይ ቸር ነው። ደጁን አጥበቀህ ያዝ።

' የሰው ልጅ ስትጠይቀው ይቆጣል። ከሪሙ ግን ካልጠየቅከው ይቆጣብሀል። '
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

28 Dec, 04:46


| ልጄ ሆይ ~3 |

< የተከዳ ልብህ። ሰዎች እንደ ድልድይ አድርገው የተረጋገጡበትን ፣ በየዋህነትህ ለዕባብ ስትቀልበው የነበረን ደግነትህ አትጥላው። አንዳንድ ትምህርቶች መራር ናቸው። ልክ እንደ መድሀኒት! ካላዋቂነት በሽታ ይፈውሱሀል ፡ ሁሉም ያንተ ልብ የተገባው አይደለም። ለራስህ አዝነህ ሰው ምረጥላት። በጨላለመ ጊዜ ክንዶቿን አጥበቀው ሚዩዙ! በሰላሙ ወቅትም እቅፋቸው ሚሞቅ። ከነውር የፀዳን ሰው ፈልግ እያልኩህ አይደለም። ሰው ነንና ጉድለት መገለጫችን ነው። ግን ደግሞ ከአድከሚው ክህደትና ራስወዳድነት ልብህን ጠብቃት። >

ውብ ማለዳ❤️‍🔥
. . .
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

27 Dec, 05:46


ጁምዓኩም ሙባረክ🖤

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

26 Dec, 17:03


አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐለይህ💚

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

26 Dec, 15:19


በዱዓችሁማ😊
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

23 Dec, 20:58


ሰላም ይድረሶት ሰላሜዋ❤️‍🔥

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

23 Dec, 19:11


አላህ❤️‍🔥 አላህ ❤️‍🔥

አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ! 🩵
ከሶለዋት አንገፍልማ!
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

22 Dec, 14:03


مناجاة آخر اليل ❤️‍🩹

#الإمام_عبد_القادر_الجيلاني
قدس الله سره 🤍
_ ሙናጃ!❤️‍🩹 የሩህ ሰላም! _
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

22 Dec, 13:55


ስክነትን ስሻ
መርጋትን ስሻ
መሸሻዬ ነው እርሱ
መጠግያዬ ነው ከትርምሱ፡
አዋጅ ለልቤ..
ሞገድ ማይንጠው ፅናትን ከሻህ
እርሱን አድርገው ሁሌም መሸሻህ፤
እርሱን ፈልጎ ፡ወደርሱ የሸሸ
ሀሉ ሰመረ እንጂ፡ መቼ ተኮላሸ?
እርሱን የከጀለ ለፍቅሩ የዋለ
መች ባ'ዘን ዋለለ?
:
ልሳኑን አቃንቶ ስሙን እየጠራ
ያደፈን ልቦናው በዚክሩ ሊያጠራ፤
የጨለመ ሩሁን
የታበየች ነፍሱን በፍቅሩ ሊገራ
የተቀማመጠ ከሙኽታሮች ጋራ፤
ራህመትህን እያለ
ራህመት የከጀለ፡
መች አፍሮ ከሰረ? መቼ ተሰበረ?
.
እጁ ሲተሳሰር ሲለው አልዘረጋ
ቃላት ሲሰወረው ልሳኑ ሲዘጋ፡
በእምባ እንክብሎቹ
የልቡን ሲያወጋ፡ መሽቶ ሚያነጋ
መች ተከፍቶ አየህ
መች ውድቀቱን አየህ እርሱን የተጠጋ!
:
[ አብዱ ሩሚ! .... 08/04/2015 ]
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

21 Dec, 10:48


ልጄ ሆይ ~2

[ አብዱ_ሩሚ ]

<  ልጄ ሆይ በጌታህ ቻይነት አትዘናጋ። በዝንግታህ ላይ ሆነህ የቀብር ልብስህን ልታጠልቅ ትችላለህና። ልጄ ሆይ! የጌታህ ቅጣት አሳማሚና ከሁሉ ሚልቅ ነው። ልብህን እንዲህ ካደነደነብህ ወንጀል መች ትታቀባለህ? መመለሻህን የሚጠባበቅ አዛኝ ጌታ ነው ያለህና ፡ ና ወደ ደጁ።
. . .
የኔ ልጅ በማዕሸር ዕለት ሰው ሁሉ የሚሸበረው ወንጀሉን አይቶ ሳይሆን የወነጀለውን ፈጣሪ ታላቅነት አይቶ ነው። የወንጀልህን ትንሽነት ሳይሆን ማንን እንደወነጀልክ አስተውል። በዚህ መልኩ ከጥፋቶች ሁሉ ልብህን ለማቀብ ጣር።
. . .
በሰላትና በጎ ነገር ላይ የምትታትረዋ ፡ ለለይል ሰላት ማትሰንፈዋ ነፍስህ የትኛው ወንጀል እንዲህ አጠወለጋት. . ? ምናልባትም 'ትናንሽ' ፡ ብለህ የናቅካቸው ይሁኑ?...
ትንሹ ወንጀልህ ፡ ልብህ ላይ ምን ያህል ተፅኖ አለው?
ትልቁ ጥፋትህ ፡  በምን ያህል እምባህ አበስከው? ነው ወይስ እምባን ተነፍገሀል? ከተነፈግክ ስለ ተነፈግከው ፀጋ ተዋደቅ። እምባን ጠይቀው! ዘለላ እምባ. .ስለ እርሱ የምትፈስ ዕንቁን >

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

21 Dec, 10:41


ልጄ ሆይ~1

[  አብዱ_ሩሚ ]

< በዚህች ምናባዊ አለም ላይ ያለን ቁስ ፈላጊ  በቁጥር አይገደብም። በውስጧ ያሉ መጋጌጫዎች ፣ ሀብትን ዝናን ፣ ድሎትና ምቿቷን ሽቶ ነፍሱን ሊመፀውት የተዘጋጀ አንድ ተብሎ አይዘለቅም። ከመሻቷ ተናጥቦ ስለ ዘልዓለማዊው አለም ፡ ስለ ሲራጥ ፣ ስለ ሂሳብ ፣ ስለ በርዘኹ አለምና ስለማዕሸር የሚጨነቅና ስለርሱ የሚለፋ ደግሞ እጅግ አናሳ ነው። ብዙኋኑ በስካር ላይ ያሉና ነፍሶቻቸው መርጋት ተስኗት የምትንገዳገድ ናት። ከኚህ አኼራዊ ሰዎች ፣ በዘመናቸው እንግዳ ከሆኑ ሰዎች በስተቀር። 
በዚህች አለም ላይ ከዱንያውም ይሁን አኼራዊ ጉዳዩች አስበልጠው አላህን(አዘ ወጀል) የሚሹና ውዴታውን የሚከጅሉ ፣ ከጥቂትም ያነሱ ጥቂት ሆነው ታገኛቸዋለህ።

ምንኖርባት ምድር አንድ ናት። አኗኗራችንና በልባችን ላይ ያለው ፍፁማዊ መሻት ግን የኑሮዋችንን መልክ ይወስናል። ታድያ የኔ ልጅ. .
የኑሮህ ቀለም በጥቁረት የተላወሰ ነው ወይስ በብርሀን የተሽቆጠቆጠ? >

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

20 Dec, 11:23


አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ🖤😊

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

19 Dec, 19:17


@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

17 Dec, 18:16


ተጓዝ . . . እግሮችህ አፈሩን ይዳብሱ
ተራመድ. . .ተመልከት ባህርና የብሱ'ን
አድማሱን . . .ፅጌውን
ጥኡም ዜማን ከአዕዋፋቱ የሚቀዳን ፡
ስሱን ንፋስ . . የማለዳን ፣

ሁሉን ቃኘው. . ሁሉን እየው ፣
መረዳት ስትጀምር ፡ የርሱን ታላቅነት ፣
ይገለጥልሃል. .
የአንተነትህ ፡  ትንሽነት ፤

| Abdu Rumi  |

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

17 Dec, 17:40


°

የልብ ጉዞ ለማድረግ ሂማ ያስፈልጋል። ከገፍላው ተነሳሽነት እንዲኖር የሚያደርገው አላህ (ሱወ) በልብ ላይ የጣለው ቀስቃሽ ስሜት ነው። ይህ አንቂ ስሜት
"ባዒስ" ይሰኛል።

ለአንድ የሰርግ ድግስ የጥሪ ወረቀት የደረሰው ሰው በቀጠሮ ሰዐት ለመሄድ ይነሳል። ድግሱን ይታደማል።
ያን ድግስ እንዲታደም ተነሳሽነት እንዲኖረው ያደረገው የጥሪዋ ወረቀት ናት።

የጥሪዋ ወረቀት እንደ "ባዒስ" ናት ጥሪው ከደረሰን ቡኋላ ለመሄድ የሚኖረን ተነሳሽነትና ለመጓዝ መሰናዳታችን ደግሞ ሂማችን ነው።

ለልብ ጉዞ ስንሰናዳ ሂማ እንዲኖረን ይህ "ባዒስ" እጅግ ያስፈልገናል።  የተነሳሽነትና የመልካም ጉጉት ስሜታችን እንዲያብብ የሚያደርገንን  " ባዒስ " በሶስት አይነት መልኩ ልናገኘው እንደምንችል አሊሞች ይናገራሉ።

አንደኛው በ #ተርሂብ ሲሆን የአላህን ቅጣት ፈርተን ካለንበት ጥፋት እንድንታቀብና በኢባዳ ላይ እንድንቻኮል ያደርገናል።

እንደ ምሳሌ አንድ ሰራተኛ በቢሮ ውስጥ በተደጋጋሚ እያረፈደ በመምጣቱ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ቢሰጠውና " ነገ ካረፈድክ ከስራ ትባረራለህ" ቢባል። ንጋት ላይ ማልዶ ቢነሳና ነፍሱ እንቅልፍ ቢያምራት እሺታውን ይቸራታል? የነፍሱን ፍላጎት ከተከተለ የሚደርስበትን ቅጣት ያውቀዋልና ነፍስያውን ተቃርኖ ከቅጣት ይድናል።

ሌላኛው መንገድ ደግሞ #ተርጊብ ይሰኛል። አላሁ (ሱወ) ለአማኞች ያዘጋጀውን ምንዳን ስናደምጥ። የጀነት ውስጥ ፀጋ. . ወንዞቹ ፣ ፍራፍሬዎቹ ፣ ሁረል ዐይኖቹ . . .የተለየዩ የማይከስሙ የአኼራ ፀጋዎችን ስናስተውል ለኢባዳ ሂማ እንዲኖረን የሚያደርገንን ባዒስ እናገኘዋለን።

ምሳሌ . . .አባት ለልጁ ይህን አመት አንደኛ ከወጣህ ብስክሌት እገዛልሀለሁ ቢለው ያ ልጅ ማጥናት ሲሰለቸው ወይም ጫወታ ሲያምረው ከጥናቱ ጀርባ የሚያገኘውን ስጦታ እያየ በነፍሱ ሳይሸነገል ሽልማቱን ለማግኘት ይጥራል።

አላህ (ሱወ) ዘንድ ስላለው ዘውታሪ ኒዕማ መስማትና ማሰብ በኢባዳችን እንዳንሰናፋና በነፍስያ መዳፍ እንዳንጨፈለቅ የሚያደርገንን ሂማ እንዲኖረን ይረዳናል።

ሶስተኛው. . . #ሸውቅ ነው። አላህን ሱወ መናፈቅ . . ማፍቀር። የዋለልንን ፀጋ በማስተንተን ፣ ፍጥረተ ዐለሙን በማጤን ፣ በተለያዩ የቁርዐን አያዎችና አሀዲሶች ውስጥ የርሱን ፍቅር መፈለግ።
የራስን ብዙ ጥፋት . . .የርሱን ሰፊ እዝነት ማሰብ።

በአንድ ጦርነት ላይ አንዲት እናት ከልጇ ጋር ትጠፋፋለች። በትርምሱ መሀል ያገኘችውን ህፃን እቅፍ አድርጋ ከደረቷ እያስጠጋች ልጇ መሆኑን ታረጋግጣለች። ካልሆነ አስቀምጣው ፍለጋዋን ትቀጥላለች። በዚህ መሀል ልጅና እናት ይገጣጠማሉ። እናት ተንሰፍስፋ ልጇን እቅፏ ውስጥ ሸሸገችው።
ይህንን ትዕይንት እየተመለከቱ የነበሩ ሰሀባዎች ልባቸው ተነክቶ አለቀሱ።
በዚህ መሀል ረሱላችን አለይሂ ሰላቱ ወሰላም ምን እንደሚያስለቅሳቸው ሲጠይቋቸው የልጅዬውና የእናቱ ሁነት እንደሆነ ይናገራሉ።
ረሱላንችንም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም " ይህች ሴት ልጇን እሳት ውስጥ ትጥላለች ብላችሁ ታስባላችሁን? " ብለው ጠየቋቸው።  በፍፁም  አንቱ የአላህ መልዕክተኛ ሲሉ መለሱ።
ረሱለሏህም " አላህ ይህች ሴት ለልጇ ከምታዝነው በላይ ለእናንተ አዛኝ ነው። " ሲሉ ተናገሩ።

ይህን አዛኝ ጌታ አዛኝነቱን ማወቅ። ችሮታውን ፣ ፍቅሩን ፣ መሀሪነቱን ፣ ሰታሪነቱን ፣ ገፋርነቱን ፣ ይቅር ባይነቱ ከልብ ማሰብ ወደ አላህ ለምናደርገው ጉዞ ሂማ እንዲኖረን የሚያደርገውን " ባዒስ"ን ይቀሰቅሳል።

ሳሊሆችን መቀመጥም ለኸያራት ሂማ እንዲኖረን ያደርገናል። ከቀደምት ሳሊሆች
" ሙሀመድ ኢብኑ ዋሲዕን ስመለከት ለወር ያህል ኢባዳ እንድሰራ በሚያስችለኝ ሂማ እሞላለሁ። " የሚል ነበር።


እንደው ስናጠቃልለው . . .
በማዕሲያ የተጠመዱ ሰዎች የሚደርስባቸውን ቅጣት በማስታወስ አልያም ለሙተቆች የተዘጋጀውን መስተንግዶን ስናደምጥ ወይም አላህን ሱወ ስንናፍቅና ከደጋጎች ጋር ስንቀማመጥ ለልብ ጉዞ የሚሆነንን ሂማ እናገኛለን።
____
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

17 Dec, 10:34


| የነፍሳችን ነፍሶች! |
ረሂመሁላህ💔

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

28 Nov, 20:02


ብኩኗ ነፍሴ . . .
ለአንዲት ቅፅበት ፡
ለአንዲት አፍታ ፡
እዚህ ስፍራ ላይ ፡ መሆን ምኞቷ ፡
ያኔ. . .
ይገታል ፡ እልፍ መሻቷ! -

አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ❤️‍🩹
ሀቢቤዋ🥺!

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

28 Nov, 18:43


|  ሩሄ ወዳንቱ ትከንፋለች🕊    |

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

27 Nov, 18:15


| ሀቢቢ ያ ረሱለላህ!💚 |

አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ አለይህ!💜
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

27 Nov, 17:08


ዝምታ. . !
:
ክርታሴ ላይ ቀለም አኖርኩ ፡
ሞነጫጨርኩ ፡
ከእምባዬ መድ እየነከርኩ ፤

ገለባዬ ከኔ በላይ ሚዛን ደፋ
ብናኝ ሆንኩኝ እፍፍ ቢሉኝ የምገፋ ፤

ቃል ቀለሙ ተደማምሮ
አልገልፅ አለኝ የሀዘኔን እንጉርጉሮ ፤
.
ከዛም. . .በዝግታ
ዘለቅኩኝ ወደ ዝምታ

ዝምታ ውስጥ ተኳለ አይኔ፡
ደማመቀ የሩህ ከውኔ

በቃል ሠጠር
ስለ ልቤ ፡ ላስስ ስጥር
( ገባኝ ዛሬ . . .)
ከቃል በላይ
ዝምታ ውስጥ
አለ ሰላም ፡ አለ ሚስጥር !
_
•[ አብዱ ሩሚ ]•
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

27 Nov, 15:06


• - ኪምያን - እንደ አላህ ፍቃድ ጊዜ ካገኘሁ ሰኞ ምንቀጥለው ይመስለኛል። ትንሽ ሀጃዎቼ ተደራርበው ነውና በዱዓችሁ! •

[ ወሰላም! ]

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

27 Nov, 04:10


| የምትወደው ነገር ሁሉ የማንነትህ ትንሹ ነፀብራቅ ነው። |

ጀላሉዲን አል-ሩሚይ💜

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

25 Nov, 08:24


| ከመሞትህ በፊት ፡ ሙት! |

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

23 Nov, 16:05


| ትርምስ ነው. . .
ግርግር ነው. . .
ፍጥረታቱ በምድር ገፅ ይራወጣል ፡
. . . ይባዝነል
ደጋግሞ ያዝናል ፡
ደግሞ ይስቃል ፡ ይፈግጋል
ስትወጣለት ትንሽ ብስራት ፡
ይዘነጋል ሺህ ስብራት !

ለመላመድ. . .
ለመዛመድ ከነፍሱ ጋር ፡
ልቡ ጠፍቶት . .
የልብ አጋር ፡
አይኑን ሰዶ ፡ ከወደ ሩቅ
ያማትራል . .
እምባ ይዘራል ፡

' ወዳጅ ' አንተ
' አካሚ ' አንተ. . .


ለዚች ልቡ ሁን ብስራት ፡
በ'አንተ' ፍቅር ፡ ነፍሱን ስራት ፣
ወዳጅ ሁናት ፡
ሰርክ ሀሴት ፡
፡ ሁሌም ደስታ
ማይደፈርስ ጥልቅ እርጋታ
የማይከስም አደይ ፌሽታ ፤

ላንዴ ይቸር ፡
እልፍ ታሟል ፡
እልፍ አምብቷል ፡
ዛሬ ይንጋለት ፡
ላንዴ ይዘንጋ ፡ ሺ ብሶቱን
ካ' ንተ ይመገብ ፡
የመሀባን ወይን እሸቱን ፡     |

[ አብዱ ሩሚ ]
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

22 Nov, 14:48


• ኪ ም ያ ~ 9 •

| አብዱ ሩሚ  |


ሸሪዓ እንደ ፋኖስ ነው። በጨለማ ውስጥ የሚዳክርን ነፍስ እየገራ ከውድቀትና ስብራት ይጠብቃል። ወደ ምንሻው ቦት ያለ ምንም መደናገር ያስጉዘናል። ግና ፋኖሱን የለገሰንን ዘንግተን ፡ ትኩረታችንን ሙሉ ፋኖሱ ላይ ማድረጋችን ወዴት ያደርሰናል?


የውሸት ተጣሪዎችና እኩይ መምህሮች ከሰማይ ከዋክብት በላይ በምድራችን ላይ ተበትነዋል። ትክክለኛ ሙረቢ ወደ ነፍሱ ባለቤት እንጂ ወደ ራሱ አይመራህም። ጣቶቹን ቀስሮ ወደ ብርሀን ሲያሳይህ ፣ የጣቶቹን ነውር አትመልከት። ይልቅ ወዳመላከተህ አይኖችህን ስደዳቸው። ትክክለኛ ሙረቢ እንደ መስታወት ነው ፡ ብርሀን ከርሱ አልፎ ወዳንተ እንዲዘልቅ በር ይሆንልሀል።

|    ኮ ብ ላ ዩ [2]    |

በእሳት የተለበለበ ፊቱን ሳይሆን በመገፋት የቆሰለ ልቡ አይኖቹ ላይ ይታየኛል። ዙሪያው ያሉ ሁሉ ለገንዘቡ የቀረቡት ናቸው። ራሱም እራሱን የሚፀየፍ አይነት ሰው ነው። በሰው ቢከበብም የሚሰማው ባዶነት አለ። ይህን ሁሉ ያወቅኩት ፡ ወደ መመገቢያው ቦታ ካመራሁ ቡኋላ እየተንደረደረ ፡ ልክ እንደ ሩቅ ወዳጁ ሲያቅፈኝ ነው።
የፊት ገፅታዬ ከርሱ የበፊት መልኩ ጋር እጅግ እንደሚመሳሰል ፈገግ እያለ ነገረኝ። የሚያወራኝ እንደ አንድ ባለ ሀብት ተኩራርቶ ሳይሆን እንደ ልጅ እየተፍለቀለቀ ነበር። ልቡ ንፁህ ነው። ኩራት ከሚሉት መርዛማ በሽታ የጠራ ይመስለኛል። ኩራት እሳት ነው። የተረገመው ኢብሊስ በአንዲት ኩራት ነው የዘመናት አምልኮው አፈር የለበሰው። ጀነት ውስጥ ኗሪ መሆኑ ፡ ከመላዒካዎች ጋር መሆኑ ፡ እጅግ አምላኪ መሆኑ ለኩራቱ ከመቀጣት አላገደውም።  ቅጣቱም እጅግ የከፋ ነበር።

አባታችን አደም አለይሂ ሰላም ጥፋት ባጠፉ ጊዜ ወድያውኑ ተውበት አደረጉ። ራሳቸውን በጥፋት ፈረጁ። ተናንሰው ወደ አላህ ተዋደቁ። ምህረቱን ለመኑት። ውስጣቸው በፀፀትና ጥርት ባለ የምህረት ተስፋ ተሞላ። መሀሪው አላህም ይቅር አላቸው። ጥፋታቸውን በይቅርታው ሻረው።

ኢብሊስ ራሱን በጥፋተኝነት አልወቀሰም። በሰራውም ስህተት ወቀሳ አልተሰማውም። ፀፀት አልነካውም። በጥፋቱ ላይ ፀና። የጥፋቱ ምንጭ ኩራት ነበርና መመለሱ ከባድ ሆነበት።

አንድ ሰውም ሲያጠፋ የጥፋቱ መነሾ ኩራት ካልሆነ ፀፀት ከልቡ ዘልቆ የተውባ እንባ ከዐይኖቹ እየረገፉ ምህረትን ለመጠየቅ ይቀርባል። የጥፋቱ ምንጭ ከኩራት ከሆነ ግን መመለሻው ዳገት ይሆንበታል።

አንድ ቀን ኢብሊስ ወደ ሙሳ(ዐሰ) መጣ። አንተ ማለት አላህ ለመልዕክተኝነቱ የመረጠህና ማናገርን ያናገረህ ሙሳ ነህ አይደል? ሲል ጠየቃቸው። ሙሳም " አዎን ማን ነህ አንተ ምንስ ፈልገህ ነው? " ሲሉ ጠየቁት። እኔ ኢብሊስ ነኝ ፡ " ከፍጥረታቶችህ መሀል  አንዱ ፍጡርህ ንሰሀን ጠይቋል።  ብለህ ለጌታህ ንገርልኝ። " ሲል ጠየቃቸው

አላህም ወደ ሙሳ (ዐሰ) ወህይን አወረደ። " እኔ የምትለውን ተቀብያለሁ ነገር ግና ሙሳ ሆይ ወደ አደም ቀብር ሄዶ እንዲሰግድ ንገረው። "
ኢብሊስ ይሄን ሲሰማ ንዴት ውስጡን ሞላው። ኩራቱ ዳግም ጠፍንጎ አሰረው።  " በህይወት እያለ ያልሰገድኩለት ከሞተ ቡኋላ እንዴት ለቀብሩ እሰግድለታለሁ።" በማለት በአመፁ ላይ ቀጠለ።

የኩራቱም ቅጣት ለዘልዓለሙ መረገም ነበር! እድለቢስነት።
ከዚህ አይነት በሽታ ልቡ የጠራችለትን ሰው ማውጋት አብዝቼ እወዳለሁ።እሱም ብዙ ዘመናት ሲናፍቀው የነበረውን ወዳጁን ያየ ይመስል ከአንዱ ጥግ ላይ አስቀምጦ የልቡን ያወጋኛል።

  
     የነበረበትን የድህነት ህይወት ያለ ምንም መሸማቀቅ አወጋኝ። ስለሰዎች ያለው ምልከታና ለዱንያ ስላላቸው የገዘፈ ቦታ በአግራሞት አወራኝ። ዙሪያው ያሉ ሁሉ ዱንያውን እንጂ እርሱን ፈልገው እንዳልተሰበሰቡ ፈገግ እያለልኝ ነገረኝ። በግራ ፊቱ በኩል ያረፈው ጠባሳ ከግራ ጆሮው አንስቶ እስከ ከንፈሩ የግራ ክፍል ይደርሳልና ፈገግታው ግማሽ ነው። ቢሆንም ግን የጥርሶቹ ንጣት ፈገግታውን ያደምቁታል። ግልፀኝነቱ ለአንድ ባዳ ሰው ሳይሆን ፡ ከዚህ በፊት ለነበረው እርሱነት የሚያወጋ ነው ሚያስመስለው።

እንዴት ከችግርና መከራ ተላቆ ወዳለበት ሀብትና ዝና እንደተደላደለ ሲነግረኝ። ልቤን ነዘረኝ። ዱንያን ስለፈቱት ሁለት ሰዎች!  ያላቸውን ሁሉ መፅውተው ከበትራቸው ጋር ስደት ስለገቡት ሰዎች! 
ልቤም ከጆሮዎቼ  ጋር ተከፍተዋል። ሚያወራውን በጉጉት ይለቅማሉ። የምሰማው ሁሉ በነበር ከሚዘገብ የቀደምቶች ታሪክ ጋር ተመሳሰለብኝ።
በወንጀል ልባቸው የቆሰለ እኚህ ሰዎች የንስሀቸውን ርቀት ታዘብኩ። ዝህድና እና አምልኮዬ ከብናኝም አነሰብኝ።
ወዴት እንደሚሄዱ ሲጠይቃቸው ፡ ያ ደራሲው የተናገረውን ነገረኝ
" . . .ብዙ ርቀን አንሄድም ! አታስብ መድረሻችን ወደ ልባችን አድራሽ ነው። የትም ይሁን ምኞታችንን ሚጋራንን እስካገኘንና ወደ ተፈቃሪያችን የሚያዘልቀንን መንገድ እጃችንን ይዞ ሚገራን ካለ እንሰክናለን። የእግር ሳይሆን የልብ ጉዞ ላይ ነን። እጅግ ርቀነው ስለ ነበረው ወዱድ ስንል ልባችን ላይ የገዘፈ ቦታ ያላትን ዱንያን መፅውተናል። በኸይር የምታውላት ይሁን! . . "

   ልቤ ክንፏን አማታች። እኚህን ድንቅ ሰዎች ለመገናኘት ጓጓች። በዘገየሁ ቁጥር ሳላገኛቸው የሚያመልጡኝ መሰለኝ። እጅግ የወደቀ የነበረ ሰው ከውድቀቱ በብርቱ ንሰሀ ሲነሳ ፡ ከሺ ደጋጎች በላይ ደግ ይሆናል። እጅግ ጌታውን ወዳጅና ፈሪ ይሆናል። እኔ እንደሁ ፡ የመንገድ ልጅ ነኝ። መሄድ አያደክመኝም።
ኮብላይ ነኝ!

የፍቅር ኮብላይ .  . .

@ktebiban_meder
__

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

22 Nov, 09:04


| ጁምዓኩም ሙባረክ🩵 |

አላሁመ ሰሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐለይህ!🩵
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

21 Nov, 13:41


•| አላህ♥️ |•

@ktebiban_meder
አላሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐለይህ!

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

20 Nov, 15:00


|      ኪ ሚ  ያ  ~8        |

-አብዱ ሩሚ-

   ብዙዎች ያኔያቸውን ይረሳሉ። በተለይም ነበራቸው ውድቀትና ድህነት ከነበር። ሰው ሀዘኑን ሽሽት ራሱን ያታልላል። ያለፈ ማንነቱን በደግነቱ ከርሱ ይወገድ ይመስል! ማጣት ውስጥ ያለው ችግር አይታየኝም። ለኔ ነፍሴን መቅጫ በትሬ ነው! ለሚቀርበኝ ፈገግታን እሰድቃለሁ ፡ አንደበቴ በዚክር የረጠበ ሆኖ ሳለ ፡ ነፍሴ እየፋፋች ስለ አካሌ መክሳት ስለምን የሁሌ ሀሳቤ ይሁን! ክምር አፈር ብቻ ነኝ! . . .!


|   ኮ ብ ላ ይ [1]    |

ይህች ነፍሴ በነጋዴዎች ከታጨቀችው መስጂድ በላይ የኮንያ ተራሮችን ትወዳለች። እዛ ድምፄን ከፍ አድርጌ አዜማለሁ። የልቤን እስክስታ አወርዳለሁ። ከተራራው አናት ላይ ሆኜ የከተማውን ትርምስ እያየሁ
" ኦ! የሰዉ ብክነት! እነዚህ ተራራዎች ላይ የሚያገኙትን ፡ የገበያ ሱቆች ላይ ለመሸመት ይተራመሳሉ! "

እውቁ የፍቅር ምሶሶ አፍጋን ውስጥ  ፡ ከበልኽ አውራጃ ሩማ ከምትባል መንደር በልጅነታቸው ወዲህ ነበር የከተሙት። በብዙ ልቦናዎች ላይ የፍቅራቸውን ችካል አኑረው ያለፉት።
እያወራሁ ያለሁት ስለ ጀላሉዲን -አል ሩሚይ ነው። ነፍሱን ለነፍሱ ባለቤት ስላስረከባት ፍጡር። ማሰቡን ትቶ ሀሳብን ስለፈጠረው ፈጣሪው ያሰበ።
በሁለቱም ክንፎች መብረር የተቻለው አፍቃሪ። ንግግሩና ግጥሞቹ በልብ የሚዳሰስ ሚስጥራትን ያጨቀ ነውና ያለ ደረጃቸው ለመረዳት በሚሞክሩት ላይ ግራ መጋባትን ብቻ ያተርፋል። ለተረዱትና በልባቸው ብርሀን ለተመለከቱት በሚስጥራት ስር ያስዋኛል።

  እኔም የእርሱ ኮብላይ ነኝ። የሩሚ ደረሳ! ምንም እንኳ ህልፈቱ ቢዘገይም አሁንም ድረስ አይኖቼ የናፍቆት እምባን ያንጠለጥላሉ። ይህ ፍቅር ነው ፡ ከኢርዙሩም ወደ ኮንያ ያመጣኝ። የኮንያ ተራራዎች ላይ ወጥቼ ስለ ወዱድ ፍቅር እንዳዜም ያደረገኝም ይሄው ፍቅር ነው። በሸይኽ ፍቅር ያለ ፈናዕ ፣ ከፍ ይልና ወደ ታላቁ ፍጡር በሀቢበላህ አለይሂ ሰላቱ ወሰላም ፈናዕ ያዘልቃል ፡ ከዛም ወደ ወዱድ!
ፈናዕ ራስን መስጠት ነው። መሻትን ሁሉ ስለተፈቃሪህ ስትል ማጣት። በተፈቃሪህ ስር አንተነትህ ደብዝዞ እርሱነቱን ማጉላት።

በሱረቱ ዩሱፍ ላይ የተጠቀሰውን አንቀፅ ላይ መክተም ነው መሻቴ። አንቀፁ የሚስር እንስቶች በዩሱፍ ውበት ተደምመው ጣቶቻቸውን በስለት ሸረከቱ። ህመሙ ግን ለአፍታ አልተሰማቸው። ነፍሳቸው በውበት ስር ሰጥማ ነበርና! ይህ ነው ፈናዕ! እኔም ህመሜን እንደሽልማት ፡ ምቆጥርበትን መቃም ላይ መደላደል ነው ምኞቴ! ጥረቴም. . . .!

በልጅነቴ ነው ስለ ፍቅር የተሰበክኩት። ያውም ከባባ ኢልያስ ውብ አንደበቶች።

< ከዘመናት በፊት አንድ ባለ ሀብት ነበር። ይህ ባለ ፀጋ ድንገት በአንዱ እለት ፡ አንዲት ውብ ባሪያን ይመለከታል። ባለ ፀጋው በውበቷ ስር ወደቀ። በነጋ በጠባ ቁጥር ምስሏ በምናቡ ይመላለሳል። ትውስታዋ ከልቦናው ሊፋቅ ተሳነው። የፍቅሯ ታሳሪ ሆነ። በፍቅርና በናፍቆት መሀል የምትናወጥ ልቡን ይዞ ወደ አሳዳሪዋ አመራ። ባሪያይቱን ከፍ ባለ ገንዘብ ሊገዛት ጠየቀው። የባሪያዋ አሳዳሪም ፡ ባለ ፀጋው ከባሪያዋ ጋር በፍቅር መውደቁን ከአይኖቹ ተረዳ። አሰብ አደረገና። " አይ በዚህ ዋጋ አትሸጥም! " በማለት ያለውን ሁሉ አስረክቦ ባሪያይቱን እንዲገዛው አደረገ። ባለሀብቱ የለበሰውንም ባርኔጣና ኩታ ሳይቀር አስረክቦ ተፋቃሪውን ይዞ ተጓዘ። >
   አየህ አይደል የኔ ልጅ! አፍቃሪ ላፈቀረው ነገር ያለውን ሁሉ ይሰዋል። ሚሰዋው ቢጠፋ የቀረችው አንዲትን ነፍስ እንኳን ብትሆን እርሷንም አይሰስትም። የርሱ መሻት የተፈቃሪው ደስታና ውዴታን መጎናፀፍ ነው። ታድያ በፍጡራን መካከል ላለ አላቂ ፍቅር ይህን ያህል ቤዛ የሚደረግለት ከሆነና ሀብትና ንብረትን እስከማጣት ካስደረሰ ፡ ስለምን የጌታህን ፍቅር ያለ ምንም ክፍያ ትሻለህ? ክልከላውን ስትዳፈር ፡ ልብህ ላይ ያለው የማፍቀር ሂማ እየሞት እንደሚጠፋ አይሰወርህ። የትዕዛዙን በትር ስትይዝ ፡ የኩራትን ኩታን ካደረግክም በራስህ ላይ የፅልመት ካባን ነው የደረብከው። እኔነትህን ጥለህ ቅረበው። መሻትህን ግደለው። ምንምነትህን ገልጠህ ፡ ከዱንያ ፍቅር ተራቁተህ ቅረበው። ጣላት ይህችን ነፍስ! ተዋድቀህ የእውነት ፡ ሚስኪንና አሳዛኝ ባሪያ ሁንለት። እንዲያ ነው ፍ ቅ ሩ ን የምታገኝ!  >

በእኚህ ቃላት ነፍሴ ተሰደደች። ተፈቃሪዋን አፍቃሪው ሰው ወደነበረበት ከተማ።
ኮንያ ከኢልምና ሲያሳ መዓከልነቷም ባሻገር ደጃፋቸው ላይ ለምንተነፍሰውም አየር ሊያስከፍሉ የሚዳዳቸው ስግብግብ ነጋዴዎችንም ይዛለች።

በእርግጥ መጥፎና ጥሩ የምንላቸው ነገራቶች ብዙ ጊዜ በጣምራ ይገኛሉ። ደግነት ካለ የሆነ ቦታ ላይ የበዛ ንፉግነት ይኖራል። ለዛም ይመስለኛል ከነዚህ ስግብግብ ነጋዴዎች አቅራቢያ የተራቡትን መቀለብያ ቤት የተከፈተው። የዚህ በጎ ስራ ባለቤት ልበ ብሩህና ቀና ሰው እንደሆነ በመሳኪኖች አንደበት ሲመሰከርለት ሰምቻለሁ። ስለ ፊቱ ገፅታ አስፈሪነትም ያንሾካሽካሉ። እኔም ይህን ደግ ሰው ላገኘው ወደ ምግብ ቤቱ ሄድኩኝ። የጠበቀኝ ግን ያላሰብኩት አቀባበል ነበር። በኺድማው ላይ ከሚሳተፉ ደረሶች ለየት ያለን ልብስ ያጠለቀ ሰው በትኩረት ተመለከተኝ። አይኖቹን ባለማመን ግራ ቀኝ አዙሮ ድጋሚ ወደኔ ተቅጣጨ።

ወዳለሁበት ስፍራ ተቻኮለ . . .

ከኮንያ ሰማይ ስር. . .
_____
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

20 Nov, 05:17


ፈገግታ

አንድ ኢማም ናቸው ይባላል... ኺድማ እማያውቁ ሰዎች መስጂድ ዘንድ ኢማምነት ተቀጥረው በእንግድነታቸው ለ3ቀናት ዳቦ በጨውዘይት ያበሉኣቸዋል
በ4ኛው ቀን በጣም ክፍት ብሉኣቸው ሱብሂ ሶላቱን እንዲህ አሰገዱ

ከፋቲሃ በኋላ " እናንተ ያመናችሁ ሰዎች ሆይ አላህን ፍሩ ፡لا تطعمو إمامكم خبزا وملحا "ኢማማችሁን ዳቦ በጨው አትቀልቡ
بل أطعموه لحما طريا فإن لم تجدو فدجاجا مشويا فإن لم تجدو فسمكا سمينا
ትኩስ ስጋን አብሉት እሱን ባታገኙ የተጠበሰ ዶሮን ይሄም ካልተገኘ ሰባ ያለ አሳን
ይህንን ያልሰራ " ዶላለን ሙቢይን" ግልጽ የሆነ ጥመት ውስጥ ነው።
በሁለተኛው ረከዐም እንዲሁ ብፌያቸውን ቀራሩ

ሶላቱ እንዳለቀ ምስኪን ምስኪን አባቶች "አፉ በሉን አፉ በሉን ሸሆቹ " እያሉ ስራቸው ተደፉ '"ምንም አይደል እንዲሁ ላስታውሳችሁ ብዬ ነው "
"ግን አንቀጹስ የትኛው ምዕራፍ ላይ ነው ያለው አላወቅነውምኮ ሸሆችዬ" ሲሉኣቸው
"ሱረቱል ማኢዳ(የማእድ ምዕራፍ)ን አጣርታችሁ ቅሩ" አሉኣቸው ይባላል።

ያው እኛም ቁርዐን እና ሓዲስ ለስሜታችን ማስረጃነት ብቻ ስንገለገልባቸው ከዚህ ኢምም ብዙም አልተለየንም........

©Aymeni

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

19 Nov, 14:44


| ኪምያ~7 |


-አብዱ ሩሚ-


አብዛኞቻችን የምኞታችን ጣሪያ ላይ ስንደላደል ሌላን ከመመኘት ውጪ ፡ ረግቶ መስከንን አንችልበትም።  ምንገታው አይነት አይደለም መሻታችን። ሁሉ በእፍኛችን ቢሆን እንኳ የማጣትን ስሜት ምንመኝ ይመስለኛል።

|     ባ ለ   ሀ ብ ቱ [2]       |

የሰው መልክ ይገርመኛል። እጅግ አስመሳይ ፍጡር ነው። የሚፈልገውን ለማግኘት ያልሆነውን ይሆናል። የማይደፈረውን ያደርጋል። የማይታሰበውን ይፈፅማል። ነፍሱ አብዝታ ለምትጓጓለት ነገር ነፍሱንም ቢሆን ይገብራታል።
ምንም እንኳ ልቤ በጥላቻና በእልህ ቢጨልምም ። አይምሮዬ ግን ንፁህና አስተዋይ ነው። የማየውን እያንዳንዱን ነገር አገናዝባለሁ። ዛሬ ላይ ስደላደል ትላንቴን አልረሳም። ከሀዲ አይደለሁም። ለራሴ እጅግ ታማኝ ነኝ።

ታድያ ዛሬ ላይ እንዲህ የከተማው ባለ ሀብት ተርታ የተመደብኩት በምፅዋት ነው ብል ማን ያምነኛል? በዛች የተባረከች የምላት ምሽት ሆዴ የረሀብ ዜማውን ሲያደራብኝ ፡ ወደ ደራሲው ቤት ቆረቆርኩኝ። ያንኳኳሁት የደራሲውን ደሳሳ ጎጆ ቢሆንም የተከፈተልኝ ግን የሀብት በር ነበር። ችግርና ማጣት ያጎሳቆለኝ እኔ ሳላመነታ ገባሁበት።  ደራሲው ከባለ ወይኑ ጋር ሆነው ለሰደቃ በጆንያ ያዘጋጁትን የወርቅ ሳንቲም በሙሉ ለኔ ለገሱኝ። የህይወታችን መልክ ተቀያየረ። ሁለቱም ተመሳሳይ ቁመት ያላቸውን በትር ፣ አነስ ያለች ቦርሳና ኢብሪቃቸውን አንጠልጥለው ለመንገድ ተሰናዱ።
የኑሮን ቀለም ተቀያየርን። እኔ ወደ ድሎቱና ምቾቱ አለም እነርሱ ወደ ችጋርና ማጣቱ ተቀላቀሉ። የሰው ልጅ ጥጋብ ይህን ያህል ይሆናል ብዬ አስቤ አላውቅም። እነዚህ በመጠጥ ሱስ የተናወዘ አዕምሮ ያላቸው ሰዎች እንዲህ ቸር ይሆናሉ ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ለጉዞ ተሰናድተው ባሉበት ፡ ወዴት እንደሚሄዱ ልጠይቅ...አልጠይቅ እያልኩ አመነታሁ።
ድንገት ደራሲው ምናልባትም ልብ አውቃው አልያም ጠንቋዩ    " ብዙ ርቀን አንሄድም ! አታስብ መድረሻችን ወደ ልባችን አድራሽ ነው። የትም ይሁን ምኞታችንን ሚጋራንን እስካገኘንና ወደ ተፈቃሪያችን የሚያዘልቀንን መንገድ እጃችንን ይዞ ሚገራን ካለ እንሰክናለን። የእግር ሳይሆን የልብ ጉዞ ላይ ነን። እጅግ ርቀነው ስለ ነበረው ወዱድ ስንል ልባችን ላይ የገዘፈ ቦታ ያላትን ዱንያን መፅውተናል። በኸይር የምታውላት ይሁን! "

  የድሎት ወራቶች ተፈተለኩ። ምቾት ላይ ስንሆን ረዥሙ ጊዜ ለምን እንደሚያጥር አይገባኝም። አልያም ችግር ላይ የሆንባት ትንሽ ሰዓት ለምን የአመታት ያህል እንደሚረዝም።  ምናልባትም በአመስጋኝነትና በታጋሽነታችን ማነስ ይሁን ነገሩ የተገለባበጠው?
ትላንት ላይ አጠገባቸው ሆኜም መኖሬን እንኳን ልብ ማይሉና ማያስተውሉ ሁሉ ዛሬ ላይ በክብር ከወንበራቸው እየተነሱ ይቀበሉኛል። አንቱታን ተቸርኩ። የውሸት ውዴታና አድናቆት ወደ ጆሮዎቼ መንቆርቆር ጀመረ።

ምንም እንኳ ከነበርኩበት የብቸኝነትና የርሀብ ዘመን የተሻለ መስሎ ቢታየኝም ፡ ቀስ በቀስ ሁሉ ነገር እየሰለቸኝ መጣ። የምኖርለት አላማ ተሰወረኝ። የቀን ጉርሴን ብቻ አግኝቼ እብቃቃ የነበርኩት እኔ ዛሬ ላይ ጠረጴዛ ሙሉ ምግብ አላረካህ አለኝ። ምን እንዳጣሁ አልገባኝም። ብቸኝነቴን በሀሰት ፈገግታቸውና ጫወታቸው የሚያሶግዱ ጊዜያዊ ወዳጆችን አፍርቻለሁ። ምመኘውና ማልመው የሀብትና ዝና አናት ላይ ተቆናጥጬ መርጋት ተሳነኝ።

  የሆነው የልቤ ክፍል ያለፈ ማንነቴ አካል የሆኑትን ማገዝ እንዳለብኝ ይነግረኛል። ስግብግቧ ነፍሴ መስጠትን እንደማጣት እየቆጠረች ትከለክለኛል። በልቤና በነፍሴ ማሀል እንደዋዠቅኩ ሁለት ድፍን አመታቶች አለፉ። የልቤ እውነት እየጎላና የነፍሴ ጥማት እየቀነሰ መጣ።

መጀመሪያ በኢዝሚር ላይ ለየቲምና ለችግርተኛ በነፃ የሚቀልብ የበጎ አድራጎት ድርጅት ከፈትኩ። ቦታውን በኢዝሚር ዳርቻ ላይ ከሚገኙ ሀሪማዎች አቅራቢያ አደረግኩት። የሀሪማው ደረሶች ያለምንም ክፍያ የቲሞችን ሊንከባከቡ ቃል ገብተው ድርጅቱን ተረከቡኝ። ትክታ የማይታይበት ፊታቸው እጅግ ሰው ይስባል። መሳኪኖችን ከምግብም ባሻገር ፍቅርና ፈገግታን ይመግባሉ። በዚህ ተግባር ላይ ከተሰማራሁባት ቀን አንስቶ መኖር ያጓጓኝ ጀመር።
ምክንያቱም ትልቅ አለማን አንግብያለሁና! የተራበን ነፍስ መመገብ። የአልቃሾችን እምባ ማበስ። የተሰበረን ልብ መጠገን። በአንዲት አማኝ ልብ ላይ ደስታን መጫር። ይህ ተግባር ከምንም በላይ ለኔ ትርጉም አለው። የመራብና የመገፋትን ጥግ አይቼዋለሁ። በርሀብ ራስን መሳት ምን ማለት እንደሆነ ፡ እየኖሩ አለመኖር። እየሳቁ አለመደሰት ፡ ሞትን በናፍቆት የመጠባበቅን ስሜት እረዳዋለሁ።

ነፍሴ በልቤ ውሳኔ ባገኘችው ሀሴት ላይ ሌላን ልታክል በኮንያና ካይሰሪም ለተመሳሳይነት አላማ ሚውሉ መመገቢያ ቤቶችን ከፈትኩ። ስክነትና እርካታ በራስ ዙሪያ ገንዘብን በማዋል እንደማይገኝ ተረዳሁ። ስክነት እንደ ወፍ ናት በተቸገሩ ሰዎች ልብ ስር  የምትገኝ። ሚያስደስታትን ስታገኝ ክንፏን እያማታች ያስደሰታት ልብ ላይ ታርፋለች።

   ገንዘብ ካለ. . .ወደ ልብ መንገድ አለ! ሆነ መርሄ። በገንዘቤ የሰዎችን ልብን መጠገኑን ተያያዝኩት። ያዘኑ ነፍሶችን ማስደሳቱን ስራዬ አደረግኩት። ምትደሰተው ግን የኔዋ ደስታ ለማኝ ነፍስ ብትሆንም።


   አመታቶች ነጎዱ! ሶስት  የድሎትና ምቾት ጊዜያቶች። ኢዝሚርን ለቅቄ ዋና ከተማ ወደሆነችዋ ኮንያ ላይ ወደገዛሁት ቤት አመራሁ። ከእለታት አንድ ቀን በከተማዋ መሀል ላይ ያሰራሁትን የመሳኪኖችን እምባ ማበሻ ቤት ላይ ግን አይኖቼ ሊያምኑት የከበዳቸውን እውነት ተመለከቱ።

. . .የ"ነበር" መልኬ!.....

@ktebiban_meder
__

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

18 Nov, 14:51


| ኪምያ ~ 6   |

- አብዱ ሩሚ -

ገፅታቸው ማይስብ ቢሆንም ውስጣቸው እጅግ የተዋበ የሆኑ ሰዎች እንዳሉ ሁሉ ፡ ልባቸው እጅግ አስቀያሚ የሆኑ ባለ ቆንጆ ፊቶች አሉ። እውነተኛ መልካችን ቢገለጥ ማን ሚቀርበን ይመስላችኀል? ምናባትም ራሳችንንም እንፀየፍ ይሁን!


|    ባ ለ   ሀ ብ ቱ [1]    |

የተራቆትኩ ነኝ። ልክ እንደ ረገፈ ዛፍ! ዕለት በዕለት እያንዳንዱ የሰውነት አካሌ ይከዳኛል። ማጣውን የማጣው ለዘልዓለም ነው። ሰዎች ከገዳይም ፣ ከአማፂም በላይ ተጠይፈው ይመለከቱኛል። አይኖቻቸው ድንገት ወደኔ ከተቅጣጨ ማን እንደሆንኩ ሳይሆን ምን እንደጎደለኝ ለማየት ያንከራትቱታል። ለኔ ፀደይ የለም ፡ ምፈካበት! ለኔ እኔው ጠበቃ ሆኜ መቆምም እስካልችል ድረስ በሰዎች ተገፍቻለሁ። እራሴንም ደጋግሜ ከመርገም ውጪ ከራሴ ጋር መታረቅ ተስኖኛል።
እኔን የተመለከቱ አይኖች ሞት በአስቀያሚ ገፅታ የቀረባቸው ይመስል ይደናበራሉ። አይኖቻቸውን ሚያሳርፉበት ሌላ ስፍራ ፍለጋ ይዟዟራሉ።
መፅዎቾቼ ፡ ፊቶቻቸውን አጨፍግገው ነው  ሽርፍራፊ ሳንቲም ሚለግሱኝ። እሱንም አሳዝኛቸው ሳይሆን ፈርተውኝ ይመስለኛል።

  
     የዛሬን አያድርገውና. . ብዙዎች የሚመኙት ውበት ተለግሼ ነበር። የዘመናችን ዩሱፍ የሚያስብልን ቁንጅና ፡ በአንድ መከረኛ ቀን አጣሁት። አካባቢያችን በሞንጎሎች እሳት በተያዛዘበት ወቅት ነው ፡ ዩስፍነቴ የረገፈው። መልከ ጥፉው እኔ የተፈለቀቅኩት።

ያ ሰዎችን ይማርክ የነበረው የላይ ገፅታዬ እንዲህ ሲቀየር የሚቀርበኝ አጣሁ። የሰዎች ውዳሴና አድናቆትን የለመደ ጆሮዬ ስድብና ማንቋሸሻቸውን መስማት ተሳነው። ክብርና ሙገሳን የለመደችዋ ነፍሴ ንቀትና ውርደትን መቋቋም አቃታት። በእሳት ከተለበለበው አስፈሪ ፊቴና ፡ ግራ እጄ ላይ ያረፈውን  ቁስል ይዤ ከኢርዝሩም ወደ ኢዝሚር አመራሁ። በአነስተኛ ንግድ የሞቀች ለአቅመ ከተማ ያልደረሰች መንደር ናት። እዚህ ማንም ስለኔ ግድ አይሰጠውም። ሁሉም ብልጭልጯ አለም ላይ ነው ልቡ ያለው። ከስንት አንዱ የተወሰነች ገንዘብ ጣል ያደርግልኛል ፡ ሌላ ከፍ ያለን ገንዘብ እንዲለግሰው በማሰብ እየመፀወተ መሆኑ ነው። በቃኝ የሌለበት ርብርብ ነው። ሁሉም ስግብግብ ነው ፡ አንድም ግን አመስጋኝ አላየሁም። ከኢማሙ ጀምሮ የአማራሪዎች ጥርቅም።

    ብዙ ጊዜ የኢማሙን ኹጥባ ከአንድ ጥግ ላይ ተሰይሜ አደምጥ ነበር። በዘመኑ ላይ ፡ በነዋሪው ላይ  ፣ በነጋዴው ላይ የኑሮ ምሬታቸውን በሀዲስ መሀል እያዋዙ ከመለፈፍ ውጪ ምን አደረጉ?
አንዳንዱ ልቡን ከጭንቀት ለማሳረፍ ወደ መስጂዱ ሲገባ ፡ ያላሰበውን እንዲያስብ እያደረጉ ፡ ጭንቀቱን ያድሱለታል።

    በእርግጥ ያሉበትን ጨለማ መርገም ትተው ፡ ጭላንጭል ብርሀን ለመለገስ ሚታትሩባት ደጋግ ሰዎችንም ትንሿ ኢዝሚር አቅፋለች። ግን ምን ያደርጋል ፡ እነርሱ ጋር ለልብ የሚሆን ቃል እንጂ ለሆድ የሚሆን ሳንቲም የላቸውም። ያገኙትን ሁሉ ላገኙት ሰው ይለግሳሉ። ስለ ነጌያቸው ብዙ አይጨነቁም።ዛሬን በደግነት ለመኖር ሲሉ ፡ ስግብግብ ማንነታቸውን እንደ በግ አጋድመውት ለማረድ ይታትራሉ። እንደ ሌላው እኔን አይጠየፉኝም። ከልብ መልካም ናቸው። ሰጋጅ ፡ ፆሚ የምላቸው ፊታቸውን በንቀት ሲያጨፈግጉብኝ ፡ እነዚህ ግን ፈገግታቸው ለልብ ይደርሳል።


በመስጂድና በሰጋጆች ፣ በሀሪማና በሙሪዶች ፣ በሱቅና በነጋዴዎች ብቻ አልታጠረችም። ኢዝሚር!
ይልቅ መጠጥ ቤት እና መጠጥ ጠጪዎቿንም ታቅፋለች። ምንም እንኳ ስለ መጠጥ ቤቱ አድራሻ የሚያውቁ ጥቂቶች ቢሆኑም መጠጥ ቤት እንዳለ ግን የአደባባይ ሚስጥር ነው።
ከመጠጥ ቤቱ ደንበኞች ውስጥ ፡ እንደሆነ የሚጠረጠረው የአንድ ደራሲ ቤት ፡ እኔ ከምተኛበት በረዳ ብዙ አይርቅም። ታድያ አንድ አንዴ በስካር መንፈስ እየለፈለፈ በሌት ወደ ቤቱ ሲዘልቅ እመለከተዋለሁ። አንዳንዴ ደግሞ በቃሉ የጌታውን ቃል በውብ ድምፅ እያዜመ ይገባል።
ይህ ፍፁም የተለያየ ማንነት ያለው ሰው ፡ ሊገባኝ አልቻለም። እንዴት ሰው በቀናቶች ውስጥ መልዓክም ሰይጣንም መሆን ይቻለዋል! ዛሬ ላይ ደግሞ ከአንድ ፈርጣማ ሰው ጋር ወደ ቤቱ በዝምታ ገባ። ያ ፈርጣማ የቤተ መፅሀፍቱ አልያም የመጠጥ ቤቱ ባለቤት ይሆናል።

ሆዴ እንደ ወትሮው መታገስ ተሳነው። ሰርክ እንደሚደለቅ ነጋሪት ይጮህብኛል። ከናፍርቶቼ ደርቀዋሉ። በእንቅልፍ ላታልለው ግራ ቀኜን ተገላበጥኩ። የሚሆን አልሆነም። ብርዱም አጥንት ይሰረስራል። ጥርሶቼ በቅዝቃዜው ሳብ ይገጫጫሉ። በመጨረሻም ያለኝን እንጥፍጣፊ ጉልበት አሰባስቤ ቅርቤ ወዳለው ቤት አንኳኳሁ።  የደራሲው ቤት!

. . ምናልባት ዛሬ የደግነቱ ተራ ይሆን? በመተስፈይ ላይ. . .

ይቀጥላል . . .

@ktebiban_meder
__

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

16 Nov, 11:31


ልጅ ናት ነፍሴ . . !

@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

15 Nov, 15:43


|        ኪምያ~5        |


-አብዱ ሩሚ-


     አዋላጆች ሚያዋልዷት ሴት ህመም ካልተሰማት፡ የልጁ መውጫ ሰላማዊ እንዳልሆነ ይገነዘባሉ። እንዲህ ነው ህይወትም ላይ ፡ እኛነታችን አዲስ ውልደትን እንዲያገኝ ህመም ግድ ይላል። ሸክላ እንዲጠነክር በእሳት ውስጥ ገብቶ እንደሚወጣው ሁሉ ፡ ፍቅርም ሚሞላው ከህመም ጋር ነው።

*

|      ደ ራ ሲ ው [2]      |


      . . .ጊዜ መውደድ ላይ ያለው ተፅኖ ምንም ነው። ለአመታት አብሮን ከሰነበተ ሰው ይልቅ ፡ ለአንድ ሰዓት ያወራነው ሰው ይበልጥ ለልባችን የቀረበ ሊሆን ይችላል።

በእምባ ብዛት ያባበጡ አይኖቼን ይዤ ወደ ባለ ወይኑ አቀናሁ። ወደ መግቢያው ስጠጋ እንደ ሁሌው ሳቅና ጫጫታ ይደመጣል። በሩን በርግጄም ብገባ ስለ መግባቴ ማንም ግድ አይሰጠውም ብዬ አሰብኩ። ለነገሩ ስለኔስ ማን ግድ ይሰጠውና! ባይሆን ባለ~ወይኑን ሰላም ብዬው እመለሳለሁ።

በሩን በቀስታ ገርበብ አደረግኩት. . .


*

አይኖቹ ከበሩ ላይ ነበር። የኔም አይኖች እግሮቼ ወደ ውስጥ ከዘለቁ ወዲህ ወደርሱ ተቅጣጭተው ነበር። ያየው እንዳስደነቀው ሰው ፊቱ በአግራሞት ተሞላ። ከሚያስተናግድበት ቦታ እየተጣደፈ ወደኔ ተቻኮለ ፡ ፊቱ ሀሴት ይረጫል። አይኖቹ አንዳች ብስራትን እንደደበቀ ያስታውቃሉ።

" ምነው ምን አጋጥሞህ ነው የጠፋሀው? " ደስታና ስጋት ያደረበት ፊቱን አስተዋልኩ።
ዝም ብዬው ወደ መቀመጭያዬ አዘገምኩኝ ፡
ተረጋግቼ ከተቀመጥኩ ቡኋላ ፡ ለአንዱ አስተናጋጅ ወይን እንዲያመጣልኝ ሲጠረው ፡ እጁን ይዤ አስተውኩት።
" ምነው ሰላም አይደለህም? " ግራ ገብቶት ጠየቀኝ።

ብልጭ ድርግም ስለሚለው ቅድስናዬ ፡ በዚህ የጥፋቴ ሜዳ ላይ ላወጋው አልፈለግኩም። የሆነውን ሁሉ ፡ ወደ ኸልዋዬ ወስጄ አስጎበኘዋለሁ። ምናልባትም ፡ የርሱም ልብ የኔን ፡ የኔን የርሱን ታቀና ይሆናል።


   ምንም እንኳን የእውነትን መንገድ ለመመራትና በርሱም ላይ ለመሰንበት ምትመኝ ልብ ብትኖረኝም። ነፍሴ ለዚህ መንገድ የሚከፈለውን ፡ የገንዘብ ፡ የፍላጎትና ምኞት እንዲሁም የነፍስን መስዋትነት ልትከፍል ፍቃደኛ አይደለችም። ልቤ የረታች ቀን ደጉ እኔነቴ ይጎላል። ሁኔታዬ ወደ ጌታዬ ያስጠጋኛል። አሳዛኝ አምላኪ እሆናለሁ። በጌታው ፍቅር እንደተነካ ከታቢም ያደርገኛል። አንደበቴ ላይ ስሙ ይገራል ፣ ያረካኛልም። መዴ ይለመልማል። ምከትበው ሁሉ ይዋባል።
ነፍሴ የምትረታበት እለት ላይ ድባቴና ምሬትን እጎነጫለሁ። የማላውቀው ብቸኝነት ይወረኛል። እንጥፍጣፊ እዝነት የሌለው ጨካኝ እሆናለሁ።  እርም የሆነውን ሁሉ እዳፈራለሁ። ጨለማ ገፄ በነፍሴ የተከተበ ድቅድቅ ነው። ብርሀኔን ለኳሽ ልቤ በፀፀት ትበራለች።


*

እግሮቻችን እየከታተሉ ፡ ከመጠጥ ቤቱ ርቀን ወደ ልቤ ጎጆ አመራን። ወደ ኸልዋዬ! ተነጥዬ ማነባበት። በፀፀት ጠብታዎች ወደረሰረሰው ምሽግ። ከነፍሴ መሻት ምደበቅበት ስፍራ!


የኸልዋው ግድግዳዎች ላይ ፡ በተለያየ ቀለም የተፃፉ ቃላቶች እጅግ ጎልተው ይታያሉ። የጌታዬን ስም በሚያማምሩ ፅሁፎች ከትቤ ፡ ከስሙ ግርጌ ፀፀቴን በቃላት ሞነጫጭርያለሁ። እምባዎቼ ግድግዳው ላይ ተዘርተዋል።
_

ወደ ኸልዋው እንደገባን ፡ ስለ እኔነቴ አወጋሁት። ሁለት ገፅ እንደሆንኩም ጭምር። በየሰሞኑ ምቀያየር ፡ ጨለማና ብርሀን የሰፈረብኝ ሰው እንደሆንኩ እየነገርኩት ሳለ . . .
" እርግጥ ብርሀንህ ፡ መርታት ሚቻላት ይመስለኛል! ብስራት አለኝ! " ሲል አቋረጠኝ።

የሚለውን ለመስማት ሙሉ ሰውነቴ ጆሮ ሆኖ የአንደበቱን ቃላት ይጠባበቅ ጀመር። ባለንበት እንደቆምን ፡ በሶስት ኩራዞች የምታበራዋ ፡ ጎጆ ስር ትልቅ ብስራትን ሊጋሩ ሁለት ነፍሶች ተሰይመዋል።

አብረን በተኛንበት ሌት ላይ ስላየው ህልም ያወጋኝ ጀመር።
". . . አይኖቿን ተከትሎ የእምባ መውረጃ ሚመስሉ መስመሮች ያሉባት ፡ ነጭ በነጭ የለበሰችመልከ መልካም ሴት አጠገብ. . ነበርክ! "

እምባዬ ያለ ፍቃዴ ረገፈ። ነፍሴ ተንሰቀሰቀች። ድብቅ ልጅነቴ ፡ ተፍለቀለቀ። የዘመን አቧራዬ ሲረግፍ ታወቀኝ ፡ ልቤን ቅልል አላት። የኔን ማልቀስ ፡ ተከትሎ እርሱም ያነባ ጀመር። እስኪበቃን ተንፈቀፈቅን. . ከዛም የለቅሶ ዜማችን ወደ ሳቅ ተቀየረ። ሁኔታችን ግራ እንደገባኝ አለሁ። ከጎጆው ግድግዳ ላይ ከዚህ በፊት የከተብኳት ፅሁፍ ተለይታ አንዲት ፅሁፍ እንደ ጨረቃ ደምቃ ታበራለች። አይኔ ፊደላቶቹ ላይ ነበር. . .

| <  በዚህች ምናባዊ አለም ላይ ያለን ቁስ ፈላጊ  በቁጥር አይገደብም። በውስጧ ያሉ መጋጌጫዎች ፣ ሀብት ፣ ዝናን ፣ ድሎትና ምቾቷን ሽቶ ነፍሱን ሊመፀውት የተዘጋጀ አንድ ተብሎ አይዘለቅም። ከመሻቷ ተናጥቦ ስለ ዘልዓለማዊው አለም ፡ ስለ በርዘኹ አለም የሚጨነቅና ስለርሱ የሚለፋ ደግሞ እጅግ አናሳ ነው። አብዛኛዎቻችን በስካር ላይ ያለንና ነፍሶቻችን መርጋት ተስኗት የምትንገዳገድ ናት። ከኚህ አኼራዊ ሰዎች ፣ በዘመናቸው እንግዳ ከሆኑት በስተቀር። 
በዚህች አለም ላይ ከዱንያውም ይሁን አኼራዊ ጉዳዩች አስበልጠው አላህን የሚሹና ውዴታውን የሚከጅሉ ፣ ከጥቂትም ያነሱ ጥቂት ሆነው ታገኛቸዋለህ።

• ምንኖርባት ምድር አንድ ናት። አኗኗራችንና በልባችን ላይ ያለው ፍፁማዊ መሻት ግን የኑሮዋችንን መልክ ይወስናል። ታድያ የኔ ልብ. . .
የኑሮህ ቀለም በጥቁረት የተላወሰ ነው ወይስ በብርሀን የተሽቆጠቆጠ? > |

አይኖቼን ከግድግዳው ላይ አንስቼ ወደ ባለ ወይኑ ላኩ። እርሱም እኔ ሳነብ የነበረውን እያነበበ ነበር። እነዚያ ፈርጣማ እጆቹ ፡ ተኮማትረው እርስ በእርስ ተቆላልፈዋሉ። አይኖቹ እምባ ያለቃቸው ይመስል ደርቀዋል። በወይን የወዙ ከንፈሮቹ ዛሬ ላይ ምድረ በዳ መስለዋል።

ፁሁፉን ያነበብነው በአይኖቻችን አልነበረም። የተገነዘብነውም በአይምሮዋችን አይደለም። ያየነውም ያነበብነውምና የተረዳነውም በልባችን ነበር። ገፀ ህይወታችን ጥቁረት ወርሶታል። ድቅድቃት ብቻ! ኋላችን የውድቀት ታሪካችን ተከትቦበታል። የክስረትና ራስን ማጣት አለም ታጭቆበታል። ሰላም የሌለው የርስክሰት ቅፅበታቶች ሰፍረውበታል።

ነበራችንን በአዲስ ገፅ ለመፋቅ ተነሳን። የነፍሳችንን ድቅድቃት በልባችን የብርሀን ሰደድ ልንረታ። ጥቁሩን ገፅ በነጭ ቡሩሽ ልንቀልም ፡  . . . .


እንደ አላህ ፍቃድ ሰኞ ይቀጥላል  . . .
@ktebiban_meder

ከጠቢባን ምድር ツ •[አብዱ ሩሚ]•

15 Nov, 11:21


• ውብ አሁን!💚

# الشخ-جابر-بغدادي🌹
@ktebiban_meder

4,549

subscribers

907

photos

236

videos