የስንብት ፅሁፍ
ክፍል-1
8ቀን እለተ እሮብ ወርሃ ነሃሴ 2016 ከቀኑ 11ሰአት ሼሆቹ እቺን አለም ትተው ተሻገሩ...
(በሰፈር 10 1446 እንደ ሂጅራ አቆጣጠር)
ትላልቆቹ ያሉፉበትን ቀን ዘግቦ ያስቀመጠ፣ ያስተላለፈ፣ ለሌሎች የተናገረ የኛ ያለፈው የሼሁ ሙሀባ እሱ ላይ ፈርድ ይሆንለታል ፦ ጀማሉ ዲን አል አንይ ኪታብ የተወሰደ...
እናም ሼሆቹ የሄዱበትን ቀን ፃፉት፣ አስተላልፉት፣ ተናገሩት ውዴታቸውን ታሸንፉበታላቹ...
ዘራቸው እንደነ አሊ ሪዳ፣ ሙሳ ካዚም፣ ጃእፈር ሳዲቅ ካሉት ከአንጋፋ አሚሮች እና አህለል ቤቶች መንገዳቸውን ጠንቅቀን ከምናውቃቸው ታብእዮችና ሰለፈሷሊሂን ይመዘዛል...
አል ጀበርትይ፣ አል በደዎይ ሲሆኑ ዘራቸው ከሁሉቱም ሰይዶች ከሰይዲ ሀሰን፣ ከሰይዲ ሁሴን ከእዝነቱ ነብይﷺ የልጅ ልጆች በጠንካራ ሰነድ ይያያዛል...
ቅም ሀያታቸው ራሙ ሙጥጥየ(ንቅየ) ጎይታ ኩየ ዘራቸው በፈትሁል ሀበሻ እንደተቀመጠው የሰይድ አህመደል በደዊ የቅርብ ልጅ የሙጃሂዱ አህመድ አል ጋዚ ልጅ ከነበሩት ሲቲ ሸምሲያ(ሹመት፣ ዡምወት)የተቀጠለው ከእነሞር ጎሳ፣ ከእንቴዘራ ጥብ፣ ቤተ እድግ ነበሩ...
ሴት ቅም አያታቸው እሜት እንደሪየትም ከጎየቶ ጎሳ ፉዱዳ ሲሆኑ ከሰይድ ከቢር ሀሚድ ልጆች ናቸው...
ቅድም ሀያታቸው እሜት አሲያ ከቸሃ ጎሳ ሲሆኑ የሰይድ እስሜኢል ጀበርትይ ዘር የሆኑት የሞገመነ ቤት ናቸው...
አያታቸው ታላቅ እናታችን እሜት አቢዳ ከጎየቶ ጎሳ ከሰይደል አሪፊን ሸኸና ኑር ሁሴን ዘር የሆኑት ዊዘረት ቤት ናቸው...
እናታቸውም እሜት ዘሀራ ከኧዣ ጎሳ እነጌየራ ጎሳ የከቢሮቹ ልጅ ናቸው...
የእናታቸው አባ ሀምዛ ኑርየ ቀድመው በአብሬትየል አወል አል ሸህ ሰይድ ባኡ ሳኒ ግዜ እስልምናን ከተቀበሉት ሲሆኑ የሸሆቹ የቅርብ ወዳጅና ሙሪድ ነበሩ...
አቦ ሀምዛ ኑርየ በባለአባትነትና በአባትነታቸው፣ በድሃ አስጠጊነትና በቸርነታቸው ይታወቁ ነበር...
በአንድ አጋጣሚ ሸሆቹ(ሸህ ሰይድ ባኡ ሳኒ) አቦ ሃምዛ ኑርየን ለመጠየቅ ወደ ኧዣ ኑር አንባ ወደሚነኘው ቤታቸው አቀኑ...
አቦ ሀምዛ ኑርየም ሸሀቸውን የሚደረገውን፣ ከሚደረገውም በላይ ሰንጋ ጥለው መውሊድ አውጥተው ተቀበሏቸው...
ማታውኑ አቦ ሃምዛ ኑርየ አንድ መናም አይተው ኖረዋል ለሼሆቹ መናሙን እንዲ ሲሉ አጫወቷቸው...
*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,
"ማታ በመናሜ አንዲት ዛፎ አየሁ... ይህቺ ዛፍ ከዛፎች ሁሉ ትሰፋለች፣ ከዛፎች ሁሉ ትረዝማለች፣ ከዛፎች ሁሉ ታምራለች፣ ከዛፎች ሁሉ ተዘይናለች... እላዩዋ ላይ የሚያማምሩ ፍሬዎች አብቅላለች... ፍሬዎቹም ከፍሬዎች ሁሉ ያምራሉ፣ ከፍሬዎች ሁሉ ይወፍራሉ፣ ከፍሬዎች ሁሉ ይተልቃሉ...
"እናም እቺ የምታምር ዛፍ ላይ እኔና እርሶ(አል አብሬትዩል አወል ሸህ ሰይድ ባኡ ሳኒ) ተቀምጠናል... ከፍሬዎቿም ሁለታችንም እየቀነጠስን አንበላለን... የፍሬዎቿም ጣእም ከፍሬዎች ሁሉ ይጣፍጣል... አንድ እንነክስ እንጠግባለን ግን አንረካም ያለ ማቋረጥ እንበላለን..."
*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,*,
አቦ ሃምዛ ኑርየ መናመን ለሼሀቸው አል አብሬትዩ አወል ሸህ ሰይድ ባኡ ሳኒ ተናግረው ጨረሱ...
ሼሆቹም አል አብሬትዩ አወል ሸህ ሰይድ ባኡ ሳኒ መናሙን እንደሚከተለው ድሩዋንም፣ ወርቋንም ፈተው ነገሯቸው... "የእኛ እና የናንተ ዘር ይቀላቀላል... እኛን የሚያስታውስ ቀድሞ ስሩ በአለመል ኑር የተደገሰለት ልጅም ይኖረናል... እኛንና እናንተን እስከወዲያኛው አለም ያዛምደናል... ተነስና እቀፈኝ አሁን ወዳጅ ብቻ አይደለንም ተዛምደናል..." ሁለቱ ታላላቅ ሰዎች ተነስተው ተቃቀፉ...
እናም የአብሬትዩ ሳኒ ሸህ ሰይድ ባኡ ሳሊስ እና የእሜት ዛህራ አቦ ሀምዛ ኒካህ ሳይተዋወቁም በአባቶቻቸው የተዛመዱ የሁለት ኒካህ ባለቤቶች ናቸው...
አላበቃሁም!!!
ይቀጥላል!!! ✍🏻በኸውላን ሰይድ