♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

@hanif_tube01


አሰላሙ አለይኩም ወራህቱላ
# @HANIF_TUBE01 channel;
ለናንተ ለቤተሰቦቹ የሚመጥን ፦
1. 💁 ❲ኢስላሚክ ringtone)
2. ‍₪አስተማሪ 🏰ታሪኮች
3. አዳዲስ〖መንዙማ₯ነሺዳ〗
4.〖ኢስላሚክ ግጥም ]]
📜ċσмιит
👇👇👇👇
@Hanif_8327
#ማሳሰቢያ:– ልክ ከሆንኩ ከአላህ ነው፤ከተሳሳትኩ ከነብስያዬና ከሸይጧን ነውና ስህተቴን ጠቁሙኝ እኔጂ " Leave' አትበሉ 🙏🙏

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

22 Oct, 16:32


💥አዎ አንቱ ነሆ የኔ ሙራድ
አንቱን ማንሳት ነው ዚክሬም አውራድ።

سيدي ﷺ

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

22 Oct, 03:53


አላህዬ በሚስት እና በ እናታችን መሃል ፍቅርን ዝራልን 🥹



ላጤ ሆነንም ዱዓችን እኮ 👌
😂

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

20 Oct, 17:50


#ቆይ ለምንድነው ሞቅ አርጋቹ ሪዓክት የማታደርጉት
ሞራል የሚባል ነገር አለኮ እስቲ ገጭ ገጭ አድርጉ ምንድነው መሰሰት😞😒
ብዙ እየለፋን ነዉ እናንተ ሪዕክት በማድረግ ደግፉን 🙁
ብዙ አዳዲስ ነገሮችን ልንጀምር ነዉ
የናንተ ሞራል ያስፈልገናል
Let's Gooooooooooo Family 👍👍

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

19 Oct, 17:05


ልባችንን ሲያቆስሉት መላኢኮችም ፅፈዉታል አላህም አይቷል💔😌

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

18 Oct, 03:23


🕌🕋 የዛሬ ጁመዓ መልካሙን ብቻ
የምንሰማበት ይሁንልን ወንድም እህቶቻችንን
አላህ ይጠብቅልን አታጉድለን ያረብ 🥺 አሚን 🤲🤲
🍁🍁

ውብ
#ጁመዓ😍
            •

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

17 Oct, 16:22


🦋🧕እብዷ ጅልባቢስት🧕🦋

☆ክፍል፡- 18☆
💥(የመጨረሻው ክፍል)💥


እንባዋም ያለ የሌለ ሀይሉን አሰባስቦ እየፈሰሰ ነው።
<<ዩስሪ ሁሉም ነገር የአላህ ቀደር ነው>>
<< አውቃለው ግን አልቻልኩም ሰአቱ ሲደርስ ፈራው ከበደኝ አስሚ>>
<<ማን ያውቃል የምትደሰችበት ቢሆንስ>>
<< አላውቅም ግን ልቤ የሚመታው ለሌላ ሰው ነው የማገባው ደግሞ ሌላ ሰው እንዴት ደስተኛ መሆን እችላለው>>
<< የአላህ ስራ ድንቅ ነው የፈለገውን ማድረግ ይቻላል>>
<<አስሚ ይሄ ሁሉ እኔን ለማዝናናት እንጂ እንደማይሆን አንቺም ታውቂያሽ ግን ብቻ ዝም ብለሽ ዱአ አድርጊልኝ የምደሰትበት ባይሆን እንኳን ለማገባው ሰው ደስታ የምፈጥር ሀቁን የምጠብቅ ሴት እንድሆን ዱአ አድርጊልኝ>>
<> እሺ የኔ ልዩ አንቺም ጠንካራ ሁኚልኝ>> ደስታ ባይሰማትም ግን እንባዋ ቁሟል። ሙሽራው መጥቶ ምሳ ከተበላ ቡሀላ ሴቶች እኛ ካለንበት ክፍል እንዲወጡ ተደረገ። ዩስሪና እኔ ስንቀር ሁሉም ወጡ። እቴቴ ሙሽራው ከመግባቱ በፊት ቀድማ ገባች። ዩስሪ እቴቴን ስታይ ቆሞ የነበረው እንባዋ መልሶ አገረሸ። እቴቴም አልቻለችም ተቃቅፈው ተላቀሱ እኔም አብሬያቸው አለቀስኩ ተላቅሰን ባይወጣልንም ሙሽራው ሊገባ ስለሆነ ራሳችንን ተቆጣጠርን። ሙሽራው ወደ ውስጥ ገባ ዩስሪ አንገቷን ወደ መሬት አቀረቀረች ሙሽራውም በርከክ ብሎ
<<የኔ ልዩ የኔ እብድ ጅልባቢስት ቀና በይ>> ዩስሪም ባለማመን በንፋስ ፍጥነት ቀና አለች ፊለፊቷ ያለው ጃድ ሳይሆን ልቧ የሚመታለት ኢያድ ነበር። ዩስሪ አላመነችም የሆነ ቅዠት ውስጥ ያለች ነበር የመሰላት። ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደ ኋላ ሸሸች።
<<እቴት እቴትዬ እየቃዠሽ አደለም ህልምም አይደለም እውነት ነው በይኝ>> ብላ እናቷ ላይ ተወሸቀች ሁሉም አልቻለም ያለቅሳል።
<<የኔ ዩስሪ አንቺ የምትወጂው እሱም የሚወድሽና በአላህ ፈቃድ የዱኒያ ብቻ ሳይሆን የአኼራም ባልሽ የሆነው ኢያድ ነው ሊወስድሽ የመጣው ህምምምም ቅዠትም ሳይሆን እውነት ነው>> ዩስሪ ከእናቷ እቅፍ ወጣችና ወደኔ ተመለከተች። እኔም ቆሜ እሷን ማየት ስላልቻልኩ ሄጄ ተጠመጠምኩባት። ለረዥም ሰአት ተቃቅፈን ተላቀስን።ኢያድ እንደተምበረከከ ነበር። እሷም ወደሱ ሂዳ ቬሎዋን ሰብሰብ አድርጋ ተምበረከከችና ፊቱን ዳበሰችው።
<< አንተ ዱዝ ሞቼብህ ቢሆን ኖሮስ ለምን እንዲህ አይነት ቀልድ ትቀልዳለህ>>
<< የኔ እብድ ሁሉም ሰው ደስተኛ የሚሆን መስሎኝ ነው ወላሂ እኔ ጋር ያለው ስሜት አንቺ ጋርም አለ ብዬ ለማሰብ ከበደኝ ግን አላህ አንቺን ለኔ እኔን ደግሞ ላንቺ ስላለን ሁለታችንም በነፍስያ ግፊያ የተለያዩ ውሳኔዎችን ብንወስንም እሱ ግን አንድ አደረገን ወደ ራስዋ ስባው አቀፈችው ሁለት የሚዋደዱ ጥንዶች እኔና እቴቴም ተቃቀፍን፡፡

ህይወት እንዲህ ናት ማጣት ማግኘት ብቻ ሁሉም አልፎ ከኢያድ ጋራ ጎጆ ቀልሰናል። የሚያምር የተዋበ የደመቀ ህይወት አለኝ አልሀምዱሊላህ ጃድና አስሚም የራሳቸውን ህይወት ሊጀምሩ ሳምንታት ናቸው የቀራቸው። ብቻ ያሁሉ አልፎ የደስታ ህይወት ጀምረናል።

<<አንቺ እብድ>>
<<ምን ላድርግህ አንተ ዱዝ>> ቸኮሌት ሳያመጣልኝ መጥቶ አኩርፌዋለው
<<በቃ ረስቼው እኮ ነው አልኩሽ>>
<< እና ምን ይሁን>>
<<ዩስሪ>>
<< አታናግረኝ>>
<<ነው>>
<<ደግሞ ካንተም ብሶ ልታስፈራራኝ ነው>> ፊቴን አዙሬ ተመቻችቼ ተቀመጥኩ። ወደ ውጪ ሲወጣም ተመልሶ ሲመጣም ሳላየው አንድ ጆግ ውሀ አለበሰኝ።
<<ዋይይይይ>> በድንጋጤ  ጮህኩ
<<ወላሂ አለቅህም>> ግማሽ ባልዲ ውሀ ይዤ ግቢ ውስጥ መሯሯጥ ጀመርን።😡
<<አንተ ዱዝ ቁም እየው ያዋጣሀል>> ሲደክመኝ ነበር ያልኩት ግን ልይዘው አልቻልኩም በመጨረሻም የተውኩት መስዬ ካረሳሳሁት ቡሀላ ውጪ በረንዳ ላይ እንደተቀመጠ አንድ ባልዲ ውሀ አለበስኩት። በቃ ሁለት እብዶች ተገናኝተን በቃ ህይወታችን ሁሉ ነፃነት የተሞላበት እብደት ሁኗል። አልሀምዱሊላህ….

💢ተፈፀመ💢

ቻናላችንን ለሁሉም ሙስሊሞች ሼር በማድረግ ስራዎቻችንን ያበረታቱ።

ከታሪኩ ምን አይነት ትምህርት እንደወሰዳቹህ ኮሜንት ላይ ፃፉልን

ሁላቹም አንብባቹ ከጨረሳችሁ እና ሌላ አስተማሪ ታሪክ ምትፈልጉ ከሆነ 👍👍👍👍👍👍 አድርጉ
shekuran😊😊

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

16 Oct, 03:26


🦋🧕እብዷ ጅልባቢስት🧕🦋

☆#ክፍል፡- 17☆

<<ከቻልሽ ሽማግዎችን እንዲልክ ንገሪው>>
<< ዩስሪ እውነትሽን ነው>>
<< አው በቃ ከዚህ በላይ ራሴንም መጉዳት ጌታዬን ማሳዘን አልፈልግም>>
<< ዩስሪ >>
<<አስሚ የምትወጂኝ ከሆነ ይህንን ብቻ አድርጊልኛ>>ውሳኔዋ ከልብ የመነጨ አይደለም የምትለውን የትዳር ህይወት ገብታበት ደስተኛ የምትሆንም እንደማይመስላት የታወቃት ተመስላለች፣ ግን የሷን መውደድ የሚገልፅልኝ ይህን ማድረግ ከሆነ አደርግላታለው፣
<< እሺ ዩስሪ ግን በደንብ አስቢበት>>
<< አስቤበት ነው የወሰንኩት>>የመጨረሻ ውሳኔዋ መሆኑን ሳውቅ ተቀበልኳት፣

በተነጋገርነው መሰረት ዛሬ ሽማግሌዎች ልጃቹን ለልጃችን ብለው እነ እቴቴ ቤት ይመጣሉ፣ ቤቱን በግዜ ፏ አድረገነዋል ዩስሪ ከአይኖቿ የእንባ ዘለላዎች ብቅ እልም ይላሉ በውሳኔዋ ደስተኛ አይደለችም፣ ግን ደግሞ በውሳኔዋ ፀንታለች እኔም አጠገቧ ሁኜ አባሽራታለውው በዚህ ሁኔታ ሽማግሌዎች መጡ ሁሉም ያለቀለት ጉዳይ ስነበር ቀጠሮ መያያዝ አልተፈለገም ነበር መጀመሪያ ሴቷ ስለሆነች ተስማምታ መፈረም ያለባት የኒካ ወረቀት ወደ ዩስሪ ጋር መጣ ዩስሪ እዚህ ላይ አልቻችም አጇ ይንቀጠቀጣል፣ እንባዋ እንደ ጅረት ይፈሳ <<ዩስሪ መጠንከር አለብሽ አንዴ ወስነሻል>> በቻልኩት መጠን አጠናክራታለው፣ እንደምንም ብላ የተፃፈውን ሳታነብ መፈረም ያለባትን ፊርማ ወረቀቱን ከራሷ አርቃ ወረወረችው፣ እኔም ወረቀቱን አንስቼው አቀበልኳቸው፣ የሁለቱ ኒካህ አልቆ ሽማግሌዎች ወጡ ዩስሪ ግን ከዛን ቡሀላ መረጋጋት አልቻለችም፣ ማልቀስ መነፋረቅ ሆኗል ስራዋ፣ ብናባብላትም ብንመክራትም ልትሰማን አልቻለችም፣ የድሮው ዝምታው ተመለሰ በመከራ የተወሰነ ቃላት የሚያወጡ አንደበቶቿ ተዘግተዋል ዝም ድጋሚ የበራ የመሰለን ጨለማ መልሶ ጨልሟል፣ ኡፍ ምን አይነት ፈተና ነው  ብቻ በአላህ ፍቃድ ህይወት ይቀጥላል፡፡

ዩስሪ ሰርግ አልፈልግም ብትልም እኛ ግን አልሰማናትም እነጃድ ቤት ሁለት ሰርግ ነው ሰብሪንም ከዩስሪ እኩል ነው የምታገባው የሰርጉ ሽርጉድ ተጀምሯል ዩስሪ ከመጀመሪያው የበለጠ ነፍራቃ ብትሆንም በሰርጓ ቀን የተዋበች መሆን ስላለባት እየወሰድኩ እስቲም አስገባታለው እንባ ያበላሸው ፊቷ በመጠኑም ቢሆን እየተስተካከለ ነው፣ ሰርጉ እሁድ ሁኖ አሁን ያለነው ቅዳሜ ላይ ነው ቬሎ ቀድሞ በሙሽራው ተመርጦ ስለነበር ሄዶ ማምጣት ብቻ ነው ዩስሪንና ሰብሪንን አንድ አይነት ሂና ማሳል ስለፈለግኩ ከሰብሪን ጋር ተቀጣጥረን ወደ ሚሳሉበት ቤት ወሰድኳቸው የሄድነው በሙሽራው መኪና ማለት የግል መኪና ነው። የነ ሰብሪን የአጎት ልጅ ነው የሾፈረው ስንጨርስ እንድንደውልለት ነግሮን ተመለሰ እኔም ከነሱ ቀድሜ ተሳልኩና እነሱ እሲኪጨርሱ ቬሎውንና የሚዜዎችን ልብስ አመጣው፣ ሁለቱም ተስለው ከጨረሱ ቡሀላ ወደየ ቤታችን ተመለስን የዩስሪ ሀዘን ቤን ለቅሶ ቤት ቢያስመስልብንም የዩስሪጓደኞችን የኔ ጓደኞች ቤቱን አሙቀውታል እሷ ግን...

ብቻ ያም ሆነ ይህ ቅዳሜም አልፎ እሁድ ደረስ ሁሉም ለበሰ ሁሉም ተደሰተ እቴቴ በየሰአቱ እየመጣች የዩስሪን ሁኔታ አይታ ትመለሳለች ድቤው ይመታል የደስታ እንጉርጉሮ ከሁሉም ሰርገኛ ይመጣል ለሙሽሪት አይኖች የማይቋረጥ ድምፅ የሎሌው እንባ ይፈሳል በአካል እኛ ጋር ብትሆንም ልቧ ግን ኢያድ ጋር ነው፣ አይ ዱንያ ሁሉም ነገሯ ተቃራኒ አለው፣ ሀዘን ስላለ ደስታ ሞት ስላለ ህይወት ማግኘት ስላለ ማጣት መሳቅ ስላለ ማልቀስ ዝና ስላለ ውርደት ወንድ ስላለ ሴት ብቻ ሁሉም ነገር ተቃራኒ አለው፣ ተመልከቱ እንግዲ በአንድ ቤት ውስጥ ሁለት ስሜት ሰርገኞቹ ደስታ ሲሰማቸው ሙሽሪቷ ግን ሀዘን ላይ ናት የሚገርማችሁ ጃድና ኢያድ እራሱ መንታ ይሁኑ እንጂ በጣም ነው የሚለያዩት የተለየ መልክ ነው ያላቸው

እያለ እያለ ከሰከንዶች ደቂቃዎችን ደቂቃዎች ሰአአቶችን ወልደው ሙሽራው የሚመጣበት ሰአት ደረሰ ሰፈሩ በክላክስ ሞቀ ደመቀ የሙሽሪቷ ልብ ከትላክሱ እኩል እየመታ ነው፡፡

#የመጨረሻው_ክፍል ❗️
☆#ክፍል፡- 18 ka 100 łįķę buhala yelaqaqal ☆

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

15 Oct, 18:06


🦋🧕እብዷ ጅልባቢስት🦋🧕

☆ክፍል፡- 16☆

በሀሳባቸው ተስማምተን ወጣን፣ ሆፒታል ደርሰን ዩስሪ ወደ ተኛችበት ክፍል አመራን ዩስሪና  እቴቴ እያወሩ ነበር
<< አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላህ>> ብዬ ወደ ውስጥ ገባ ሁለቱም በአንድነት መለሱ፣
<<እንግዳ ወደ ውስጥ ለመግባት ፍቃዳሁችን ይጠይቃል፣>>ስል ዩሪ ግራ የተጋች ትመስላለች እቴቴ ግን ስለነገርኳት ብዙም ሳይገርማት፣
<< ይግቡ ቸግር የለውም>> አለች እነ ሀጂም ወደ ውስጥ ገቡ ዩስሪ በአንዴ ፊቷ ተቀያየረ እንባዋ ከየት መጣ ሳይባል በአንዴ እንደ ዥረት ወረደ ኢያድን ያሳጣት ጃድ እንደሆነ ነው የምታስበው፣ እኛ ሰዎች ስንባል ሁሉንም አድራጊ አላህ እንደሆነ የምናምነው በደስታ ግዜ እና የምንፈልገው ሲሆንልን ግዜ ብቻ ነው በሀዘንና የምንፈልገውን ስናጣ ግን የአላህን አድራጊነት እንዘነጋለን፣ ግን ለምን በሁሉም ለማግኘትም በማጣትም በደስታም በሀዘንም የአላህን አድራጊነት መዘንጋት አይኖብንም የሰው ልጅ ምንም የማድረግ ሀይልም ቁዋም የለውም ከአላህ በቀር ይህንን ልናስተነትንና ልንገነዘብ ይገባል፣ ለማንኛው ዩስሪም የአላህን አድራጊነት ረስታ ይህ ሁሉ የተፈጠረው በጃድ ምክንያት እንደሆነ ታስባለችች ለዛም ስታየው ተናዳለች፣ የድሮውን ትዝታዋን ቀሰቀሰባት አቅጣጫዋን ቀይራ ፊቷን ወደ ግድግዳው አዞረች፣ ጃድ ሁኔታው ስለገባው፣
<<ዩስሪ በአላህ አፉ በይኝ ወላሂ እኔ አውቄው የተፈጠረ ነገር አንድም ነገር የለም፣ ሁሉም የአላህ ቀዳ ነው አሁንም ቢሆን አልረፈደም ሁሉም ነገር በአላህ ፈቃድ ይስተካከላል>> መልስ አልሰጠችውም ሀጂም ቀጠል አድርገው
<< የኔ ልጅ ለምን እንደዚህ ትሆኛለሽ ሁሉም ነገር ባንቺ አልተጀመረም መውደድም መወደደድም ከአላህ ነው ደግሞ ሁል ግዜም ማስታወስ ያለብሽ አንቺ ስላቀድሽና ስላሰብሽ ሳይሆን የሚሆነው አላህ የቀደረው ነው፡፡
አሁን ሁላችንም እውነቱን አውቀናል በተቻለን መጠን በአላህ እገዛ ሁሉም ይስተካከላል ግን እስከዛው ራስሽን ማጠንከር አለብሽ ለምን ለባሪያው ብለሽ ፈጣሪሽን ታስቆጫለሽ ለምን ቢያንስ ኢያድ ሁሉንም መሸከም አቅቶት ከዚህ ባይሄድ ኑሮ ሁሉም ነገር ግልፅ አይመጣም ነበር አላህ ሁሉንም የሚያደርገው ለኸይር ነው አይደለም እነዴ>>ሶስታችንን አዩ እኛም አንገታችንን ወደለይና ወደታች በመነቅነቅ አረጋገጥንላቸው ዩስሪ ግን ፊቷን አዙራ ከማልቀስ ውጭ የመለሰችው ነገር የለም
እነ ሀጂም ያለችበትን ሁኔታ ስላወቁ ያን ያክል ሊያስጨንቋት አልፈለጉም ከኛ ጋር ትንሽ ትጫውተው ወጡ፡፡

ቀናት ቀናትን ወልደው ዩስሪ ከሆፒታል ከወጣች ሳምንት ሆናት፣ የሀጂ ምክር ትንሽ ሳይለውጣት አልቀረም፣<< ግን ለምን እውነትም ለምን የአላህን ውሳኔ መቀበል አቃተኝ ለምን ጠንካራ መሆን አቃተኝ ኢያድም ቢሆን ርቆ የሄደው ለኔ ስላልተፈጠረ ይሆናል>> የምትደጋግመው አረፍተ ነገር ነበር፣
ወላሂ ያለ ዩስሪ ቤቱ በጣም ነው እንደ በረዶ የቀዘቀዘው ቤት ሲቀዘቅዝ በቡናው በእሳት ይሞቅ ይሆናል ይሄ ግን ማገዶ ቢቃጠል ቢቀጣጠል የማይሞቀው ቅዝቀዜ ነው፣ ዩስሪ አሁን ላይ መንቀሳቀስ ጀምራለች፣ ምግብም በትንሹም ቢሆን መመገብ ጀምራለች፣ ብቻ አልሀምዱሊላህ

ዩስሪ ዛሬ ብቻዋን ፀሀይ እየሞቀች ነበር ከእቴቴ ጋር ስራችንን ሰርተን ከጨረስን ቡሀላ ሄጄ አጠገቧ ተቀመጥኩ፣
<<አስሚዬ>>አለችኝ
<< ወዬ፣>>
<<እኔ እኮ አላህን አሳዝኜዋለው>>
<<እንደዛ እያልሽ መፀፀት ሳይሆን አስከፍቼዋለው ብለሽ የምታስቢ ከሆነ ያስፋሽበትን ጥፋትሽን ለመካስ ሞክሪ ሁሌም ተውበት አድርጊ አላህ ተመላሽ ባሮችን ይወዳል>>
<<እኮ እኔም እኮ የምልሽ ይሄንን ነው ጃድም በኔ እንዲጎዳ አልፈልግም ምን አልባት ጃድ ከሆነስ ለኔ የተፈጠረው የጌታዬን ምርጫ መጋራት ስለማልፈልግ የጃድን ጥያቄ መቀበል ፈልጋው ከቻልሽ ሽማግዎችን እንዲልክ ንገሪው>>

☆ክፍል 17 ይቀጥላል☆.....

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

15 Oct, 14:45


ሀበሻ የአለም ኢጅቲማ ጥቅምት 14_17 በቡታጀራ 🔊🔊

ታላቁ የአለም ኢጅቲማዕ በውቢቷ ቡታጅራ ከጥቅምት 14_17 #የአለም_አሚር_ሸህ_ሰአድ ሀፊዘሁላ ጨምሮ ከ80 በላይ የአለም ሀገራት ጀመአዎች የሀገራት አሚሮች አህለል ሹራዎች ኡለሞች ቁደሞችን እየላኩ ይገኛሉ ልቡን አንድ አድርጎ ስለ ኡመቱ ይወያያል ዱአ እና ዳዕዋ ያደርጋል ሙሀባ ይዘንባል የአላህ ራህመት ይወርዳል ሂዳያ ራህመት በረካ ከሀበሻ ጀምሮ አለም ላይ ይወርድ ዘንድ ይከጀላላል
እኛም ኢማናችን አዕማላችን አማናችን ይታደሳል ኢንሻአላህ

ከኢጅቲማው በፊት ፊሰቢሊላህ መውጣት ለኢጅቲማው ሩህ ነውና በቻልነው ኹሩጆችን እንውጣ በትንሹ 3ቀን ወጥተን ኢማናችንን አድሰን ለኢጅቲማው ሩህ እናበጅለት

ሰይዳችን(ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) 124ሺ ሰሃቦቻቸውን ሙሉ ኢጅቲማዕ ሰብስበው ነበር ሰሀቦቹም ዳዕዋ ለማድረግ በአለም ላይ ተበትነው ነበር እኛም ኢንሻአላህ ከኢጅቲማው በኋላ አለምን እየዞርን ዳዕዋ የምናረገበትን እድል አላህ ያመቻችልን

ይሄን መልዕክት ላልደረሳቸው አድርሱልኝ

ቡታጅራ አንቀርም እዛው እንገናኝ👐💚

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

15 Oct, 14:09


ታቢዒዩ ሳቢት ለአነስ (ረ.ዐ) ...
"...አነስ ሆይ የአላህ መልክተኛን (ሰ.ዐ.ወ) እጅ በእጅህ ነክተከዋል እንዴ? ..." ሲል ጠየቀው...
አነስም(ረ.ዐ) "...አዎ..." ሲል መለሰ
... ታቢዒዩ ሳቢትም በናፍቆት እና በፍቅር ስሜት ውስጥ ሆኖ እንዲህ አለ ...
"...እስኪ አሳየኝ ልሳመው ?!..."🥹

اللهم صلِ و سلم و بارك على سيدنا محمد ﷺ 💚

صلو

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

14 Oct, 16:51


🦋🧕እብዷ ጅልባቢስት🧕🦋

☆#ክፍል፡- 15☆
 
እኔም በጣም ተደናግጫለው አላውቅም ዩስሪ ብትሞት ምን እንደምሆን አላውቅም ማሰቡን እራሱ አልፈልግ እየሮጥኩ ወጥቼ ጎረቤቶችን ጠራኋቸው አንዱ መኪና ነበረውና ይዟት ወደ ሀኪም ቤት ከነፈ፣

ሀኪሞቹም ወድያው ወደ ድንገተኛ ክፍል ይዘዋት ገቡ እቴቴ አብራ ለመግባት ብትሞክርም ከለከሏት፣ ኢላሂ የዛሬን አትርፋት እንጂ ሁሉንም ለጃድ ነግረዋለው ቢያንስ የኢያድን ድምፅ መስማት ለሷ አንድ መድሀኒት ነው፣ ከትንሽ ቆይታ ቡሀላ አንድ ዶክተር ከድንገተኛ ክፍል ወጣና የዩስራ ቤተሰብ ብሎ ተጣራ እኔና እቴቴ ተሯሩጠን ሄድን እቴቴን<< አንቺ ምኗ ነሽ>>አላት
<< እናቷ ነኝ፣ >>ስትለው
<<ጥሩ ተከተይኝ>>ብሏት እኔን ደግሞ
<< አንቺ 7 ቁጥር ሄደሽ ካርድ አውጪ>>አለኝ
እቴቴ ተከትላው ሄደች እኔ ደግሞ ካርድ ለማውጣት ወደ 7 ቁጥር ሄድኩ ስመለስ ገና እቴቴ አልወጣችም ወዴት እንወሰዳት ስላላወኩ ከአንዱ ወንበር ላይ ተቀመጥኩ ዶክተሩ ምንም ፊቱን ቢያጨማድድም የመሞት ወሬ ስላላነሳ ውስጤ ተረጋግቷል፣ ትንሽ እንደተቀመጥኩ እቴቴ መጣች፣
<< እቴት ምን አሉሽ >>መልስ ሳትሰጠኝ በረዥሙ ተንፍሳ አጠገቤ ተቀመጠች፣
<< በአላህ እያስጨነቅሽኝ ነው የሆነ ነገር በይኝ>>
<<አስሚ ዩስሪ አቅም በጣም ነው ያነሳት ምግብ አለመብላቷ በጣም ጎዶቷታል በዚህ ላይ በዚህ ላይ አብዝታ የምታስበውና የምትጨነቀው ነገር በዚው ከቀጠለ ጭንቅላቷ ላይ ሌላ ችግር ሊያመጣ ይችላል፣ እናት ሁነሽ ይህን ያህል እስክትሆን ምን ትጠብቂያለሽ አለኝ እውነቱን እኮ ነው እንዴት የአንዷን የልጄን ህይወት ማስተካከል ያቅተኛል>>
<<እቴት አንቺ ያጠፋሽው ጥፋት የለም አስሚ ቀድማ እንደምትወደው ብትናገር ይህ ሁሉ ባልተፈጠረ ብቻ አልሀምዱሊላህ አሁን ጤናዋ ይመለስ ሁሉም ነገር ይስተካከላል>>አልኳት ለማፅናናት ያክል
እኔ ብዙ ግዜ ሰዎችን የማልቀርበው ለዚህ ነው ሰው ሆኖ ሙሉ የለም ያስደሰተን ይመስለውና ይጎዳናል አንዱን ለማዳን አንዱን ይገላል ብቻ ሰዎች ሁሌም አያስደስቱንም

ዩስሪ ከድንገተኛ ክፍል ወታ አልጋ ይዛለች እቴቴን ከዩሰሪ ጋር ትቼ ጃድ ጋር ሄድኩ ሱፐር ማርኬት ማለት
ሀጂ ሲያዩኝ በጣም ነበር ደስ ያላቸው
<<አሰላሙ አለይኩም >>አልኩ ከበር <<ወአለይኩሙሰላም አስማ ግቢ>>
የቢሮዋቸው በር ላይ ነበር የቆምኩት ወደ ውስጥ ገባው ጃድም አንድ ላይ ነበሩ፣
<< አስማ ዩስሪ ምን ሁና ነው ቢያንስ እንኳን ስራ ያቆመችበትን ምክንያት  ማወቅ የለብንም ነበር፣>>
<<ልክ ነው ሀጂ ግን አንድ አንድ ምክንያቶች ለመናገር አቅም የማይሰጡ ናቸው፣>>ስል ጃድ፣
<<ቢያንስ ምክንያቱን ባትናገር ስራ ልታቆም እንደሆነ መናገር ነበረባት፣>>
<<አው ይህ ጥፋት ነው በሰአቱ ግን ማንም ቢሆን ይህን የማድረግ አቅም አይኖረውም>>
<<ይህን ያህል አቅም ያሳጣት ምንድነው>>ሀጂ ጠየቁኝ ከጅምሩ እስከ ፍፃሜው ነገርኳቸው ኢያድም ርቆ የሄደበትን ምክንያት አሁን ዩስራ ያለችበትን ሁኔታ አንድም ሳስቀር ነገርኳቸው፣ ጃድ ስሜቱን መቆጣጠር አልቻለም፣
<<እንዴት የወንድሜን ስሜት መረዳት አቃታኝ ደግሞ ስለራሷ አደራ ሲለኝ እንደሚወዳት ለምን አልተረዳውም እሱ የኔን ስሜት ተረድቶ እሱ ሁሉንም ነገር ትቶ ለኔ ብሎ ርቆ ሲሄድ እኔ እንዴት መረዳት አቃተኝ፣>>ጠረቤዛውን በቦክስ ነተረው
<<ጃድ ተረጋጋ ሁሉም የአላህ ውሳኔ ነው ባይሆን አሁን እኔ የመጣሁት እንድትቆጭና እራስህን እንድትወቅስ ሳይሆን ኢያድን ቢያንስ በስልክ የምታገኘው ከሆነ መቶ ነገራቶችን እንዲያስተካክል ልትነግረው ይገባል ዩስሪን እኔ ከነገርኩህ በላይ መተህ ብታያት ታዝንላታለህ>>አልኩት ሀጂም ፣
<<ልክ ነው ባይሆን አሁን ምን አይነት ሁኔታ ውስጥ ናት>>
<<አሁን ምንም አትልም ሀጂ ግን  ሆስፒታል አልጋ ይዛለች ሀኪሙም የምትጨነቀውን ነገር  ካላቆመች፣ ጭንቀቷ ወደ በሽታ እንደሚቀየር ነግሮናል ጭንቅላቷ ላይ የከፋ ነገር ሊያጋጥማት እንደሚችልም አበክሮ ነግሮናል ስለዚህ በተቻለ መጠን ኢያድን ወደዚህ እንዲመጣ ቢደረግ ካልሆነም ግን ወይ በስልክ የምታናግርበትን እድል መፍጠር አለብን እባካችሁ እህቴን ላጣት ነው>>ስል፣ ጃድ ስልኩን አውጥቶ ወደ ኢያድ ይመስለኛል መደወል ጀመረ ግን ስልኩ አይነሳም ደጋግሞ ቢደውልም አይነሳም፣
<< በቃ ተወው ሲያየው ይደውላል አሁን የተኛችበት ሆስፒታል ሂደን ልንዘይራት ይገባል>> አሉ ሀጂ …. ጃድ………

☆#ክፍል_16_ይቀጥላል☆....

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

13 Oct, 17:13


¤ የሆኑ ትዝታዎች አሉ ስናስባቸው መጥፎ ስሜትን የሚያመጡ...😞
ግን ደስ የሚሉ😊
እነርሱን ማሰብ ሀጢአት የሚሆንበት ጊዜ አለ🥺
ለትዝታም ማማር ለካ ጊዜ ይወስነዋል።😔

የገፋናቸውን ማስታወስ😞
የገፉንን ማሰብ😔
የተንከባከቡንን🥹
የጠበቅናቸውን ብቻ ከትናንትም ለካ ይመረጣል።🥹🥹

❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

12 Oct, 17:46


🦋🧕እብዷ ጅልባቢስት🧕🦋

☆#ክፍል፡- 14☆

የኔ እብድ እኔ ደካማ ባሪያ ነኝ በፍቅርሽ ተጎድቻው ግን ላንቺ እኔ አልገባሽም፣ ደግሞ ይህንን ስልሽ በራስሽ ለመናደድ እንዳትሞክሪ ምክንያቱም የሚሆነውን ነገር ስለወሰንኩ ምን አልባት እኔም እንደምወድሽ ጃድ ቢያውቅ ይህ ክስተት ባልተፈጠረ ነበር፣ አላህ ካለ በቅርቡ ሽማግሌዎች ወደናንተ ቤት ይመጣሉ ለወንድሜ ሊጠይቁሽ፣ ገግን እንቢ እንዳትይው እሺ 
እኔ ከናንተ መራቄ ጥሩ መስሎ ታየኝ ሁለታችሁ አንድ ላይ መሆናችሁ ቢያስደስተኝም ግን ደካ ነኝና የምቋቋምበት አቅም ስላጣው ርቄ መሄድን መርጫለው አላህ ካለ ስትጨነቂ ያደርሽበትን ሌሊት ጉዞ ላይ ነኝ፣ ደግሞም ስመጣ አንቺና ጃድ ልጅ ወልዳችሁ ልጆቹን መሳም ነው የምፈልገው፣ እባክሽ በውሳኔዬ እንዳትበሳጪ ለኔም ላንቺም ለጃድም የሚጠቅመን የኔ ርቆ መሄድ ነው፣ ደግሞ በደንብ ያልተሰናበትኩሽ አጠገብሽ ሁኜ ሰሜቴን መቆጣጠር አልችልም እንባዬ ይቀድመኛል ለራሴም ተከፍቼ አንቺን ማስከፋት አልፈልግም የኔ እብድ ላንቺ የሚገባሽ በደስታ መኖር ነው በቃ ልክ እንደ ድሮው፣ ደግሞ ስለ ቸኮሌትሽም ስለ ወተትሽም ለጃድ ነግሬልሻለው ደግሞ መጠሪያዬን ዱዝ ለማንም እንዳትሰጪብኝ እሺ ሁሌም የአላህ ጥበቃ አይለይሽ የተዋበና የደመቀ ኑሮ ኑረሽ የልጅ እናት ሁነሽ ተመልሼ እንደማይሽ ባለ ተስፋ ነኝጨመልካሙን ሁሉ እመኝልሻለው>> እህህ የኔን ህይወት አጨልሞ የራስን ህይወት ማስተካከል ምን የሚሉት እብደት ነው እኔም እኮ እወደዋለው ቢያውቅ እንደውም እሱም ከሚወደኝ በላይ ቆይ ምን አይነት አስተሳሰብ ነው ያለው፣ እንዴት ነው አሁን እኔ የምሆነው ለምን ብቻውን ይወስናል ቢያንስ ቢያማክረኝ
ምን ችግር አለበት፣
*
በጠዋቱ እቴቴ ደወለችልኝ፣
<<ሄለው አስሚዬ አሰላሙ አለይኪ>>
<< ወአለይኪሰላም እቴት እንዴት ነሽ>> <<አልሀምዱሊላህ>>
<<ኧረ ጓደኛሽ ዝም ብላ እያለቀሰች አይኗን ልታጠፋ ነው ነይና መላ በያት>>
<<ምነው የተፈጠረ ችግር አለንዴ>>
<<ኧረ ምን አውቄ>>
<< እሺ በቃ መጣው>> ግዜ ሳላጠፋ ወደነ ዩስሪ ቤት ሄድኩ ክፍሏ ስገባ ድምፅ የሌለው እንባ ታነባለች፣
<<ዩስሪ>>ዝም፣ <<ዩስሪዬ ምን ሁነሽ ነው እቴቴን እኮ እያስጨነቅሻት ነው>> ስላት የሆነ ወረቀት ከመሬት አንስታ ሰጠችኝ አነበብት ከኢያድ ነበር፣ሳነበው በጣም አሳዘነችኝ ዩስሪ ኢያድን እንደምትወደው ባትነግረኝም ከሁኔታዎች እረዳ ነበር ታድያ ይህ ሰው ርቆ ሂዷል ሂዳ እንዳትመልሰው ማታውን በሯል፣
<< ዩስሪዬ ሁሉም ነገር ቀደር ነው በዚህ ደግሞ ታምኚ የለ>>አታወራም ብቻ ዝም ብሎ ማልቀስ ነው፣ ግራ ገባኝ እቴቴ በጣም ተጨንቃለች እሷም ቀድማ አንብባው ነበር፣
<<ዩስራ እቴቴ በጣም ተጨንቃለች ቢያንስ ለሷ ብለሽ ጠንካራ ሁኚ>>መልስ የለም፣ ብዙ ግዜ በህይወታቸው እየተዝናኑ እየሳቁ የሚኖ ሰዎች ትንሽ ነገር ይጎዳቸዋል በርግጥ ይሄ ትንሽ ነገር ሆኖ ሳሆን ግን በቃ መቋቋም አልቻለችም፡፡

ዩስሪ ከዛን ግዜ ጀምሮ ወደ ስራ ሄዳ አታውቅም ጃድ ምን እንደሆነች ቤት መጥቶ ጠይቋት ነበር እሷ ግን ልታየው ፍቃደኛ አይደለችም፣ እኔም በሷ ምንያት ወደ ስራ ሂጄ አላውቅም ዩስሪ ምግብ ትታለች አትበላም በግድ ለእቴቴ ብላ አንድ ሁለት ብትጎርስ ነው ያቺ ፍንድቅድቋ ዩስሪ የለችም ቤቱ ያለሷ ጨለማ ለማንም በዚህ ምክንያት እንደታመመች እንዳንናገር ቃል አስገብታናለች።ቢያንስ ብናወራ በተለይ ለጃድ ባስረዳው ኢያድን ምናገኝበት መንገድ መፍጠር እንል ነበር።ያአላህ ብቻ ሁሉንም ገር ያድርገው እንጂ በዚው ከቀጠለች ለህይወቷም ሰጋለው።በዚህ ላይ ከሰውነት ጎዳና ወታለች

አንድ ቀን ከእቴቴ ጋር ቁርስ ሰርተን ዩስሪን ለመቀስቀስ ወደ መኝታ ቤቷ ስገባ ዩስሪ በሩጋራ ወድቃለች፣
<<ዩስሪ ዩስሪ ኧረ ዩስሪ>> ጮሄ ብጣራ አትሰማኝም እቴቴም ጩኸቴን ሰምታ መጣች የእናት ነገር በጣም አለቀሰች የሞተች መሰላት……..

☆#ክፍል 15 ይቀጥላል☆...

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

12 Oct, 04:10


ፈገግ በሉ...😄

አንዷ ናት አሉ...

ዩሱፍና አብደረህማን የሚባሉ ሁለት ልጆች አሉኝ ። ተኮርፈው  አብደረህማንን ዩሱፍን ሲያሰግደው

ሁሌም ይህንን አያ መቅራት ያበዛል

اقتلوا يوسف أو أطرحوه أرضا" 😁
ዮሱፍን ግደሉት ወይም መሬት ላይ ጣሉት”😂😂


صباح الخير🌞
❥❥нαйιƒღღ🫶

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

11 Oct, 17:08


🦋🧕እብዷ ጅልባቢስት🧕🦋

☆#ክፍል፡- 13☆

ሰብሪን ሰርጌ እንኳን እስኪያልፍ ብላ ለምናኝ ነበር ግን እዚህ ቁጭ ብዬ ውስጤን እያስከፋሁ በእድሌ እየተማረርኩ ጌታዬን ከማስቀይም ርቄ መሄድን መርጫለው፣ እንደምንም እራሴን አረጋግቼ ወደ ጃድ መኝታ ቤት ሄድኩ

<<ወንድሜ>>
<< አቤት፣ ዩስሪን ተንከባክበህ አኑራት እሺ ትንሽ ነገር ነው የሚያስፋት ደግሞ አብራችሁ መኖር ስትጀምሩ ይበልጥ ትወዳታለህ ዘና እያደረገችህ ነው የምትኖሩት እኔ ከሄድበት ስመጣ ልጃችሁን መሳም ነው የምፈልገው፣ ደግሞ ጋላክሲ ቸኮሌት ሁሌም ማታ ማታ ስትገባ ይዘህላት ግባ አንድ አንዴም እያወጣህ አዝናናት ማንኛውንም ምግብ ስትበላ ወተት አብሮ ቢኖር ደስ ይላታል እሱም ከቤታችሁ እንዳይጠፋ፣ ለሁለታችሁም ያማረና የተዋበ ዘውጅን እመኝላችኋለው>> ከዚህ በላይ ማውራት አልቻኩም እንባ ስለተናነቀኝ፣
<<በቃ ተኛ ሳልነግርህ እንዳልሄድ ብዬ ነው ደና ደር>> ከክፍሉ ወጣውና ወደ ክፍሌ ሄድኩ ረከአተይን ሰግጄ ለሁለቱም የተዋበ ትዳር ህይወት እንዲሰጣቸው ዱአ አድርጌ ወረቀት ላይ የሆነች ነገር
ጫር ጫር አደረግኩ
*
ዛሬ ኢያድ በግዜ አልመጣም ወደ አስር አከባቢ መጣ
<<አሰላሙ አለይኪ>>
<<ወአለይከ ሰላም አንተ ዱዝ በቃ እንደፍላጎትህ ነዋ የምትኖው>>
<<ማለት>>
<<ማለት ይለኛል እንዴ ደግሞ ቢያንስ ስትቀር ቀርቻለው አልተመቸኝም ይባላል ወይ እኔ እንዳልደውል ስልክህ አይሰራም>>
<< የኔ እብድ የሆነች ጉዳይ ገጥማኝ እኮ ነው>>
<< ቢሆንም ወይ መናገር ወይም ስልክ መክፈት በል አሁን አታስለፍልፈኝ ቸኮሌቴን አምጣ>> ፈገግ ብሎ
<<በቃ ቁጣሽ ከዛ አይዘም>>
<<ለኮሌት ማለት እኮ ልክ በሚቀጣጠል እሳት ላይ ውሀ ስትጨምር እንደሚጠፋው ለኔም ቸኮሌት ስትሰጠኝ እበርዳለው>>
<<ስለዚህ ሁለተኛ እንዳትናደጂ>> ብሎ 3 ካርቶን ቸኮሌት ሰጠኝ
<<እንዴ እንድሸጠው ነው>>
<<እንደተመቸሽ የሚያስደስትሽን አድርጊ ባይሆን የጀመርኩት ስራ ስላለ ልሂድ>> ብሎ አንገቱን ደፋ እንባ ከአይኑ ግጥም ሲል ይታየኛል፣ ከኪሱ ወረቀት አወጣና<<ጠዋት ከፈጅር ሰላት ቡሀላ አንብቢው መልካም ግዜ>>ጥሎኝ በፍጥነት ወጣ

የሆነ የተደበላቀ ስሜት ነው የተሰማኝ ከስራ ወጥቼ ከገበሁ በኋላ እራሱ ምንም ልረጋጋ አልቻልም እቴቴም አስሚም ምን እንደሆንኩ ይጠይቁኛል፣ ግን ምን ብዬ መልሳለው ምን እንደሆንኩ እኔ እራሱ አላውቅም ወደ መኝታዬ ከሄድኩ ቡሀላ እንቅልፍ አጣው ብገላበጥ ብገላበጥ እንቅልፍ የሚባል አጣው፣ የሰጠኝን ወረቀት ለማንበብ አወጣውና ደግሞ መልሼ አስቀምጠዋለው ሌቱ አልገፋ አለ ፈጅር ራቀብኝ እንቅልፍ እንቢ አለኝ የማያልፍ ነገር የለምና ሰአታት አልፈው ፈጅር አዘነ ግዜ ሳላጠፋ ወረቀቱን
ከፈትኩት
<<አሰላሙ አለይኪ ወራህመቱላ ወበረካትሁ፣ የኔ እብድ ይህን ወረቀት ከሰሰጠሁሽ ሰአት ጀምሮ እስክታነቢው ድረስ እንደምትጨነቂ አውቃለው፣ ግን ቀድመሽ ካነበብሽው ለውሳኔዬ እንደምታደናቅፊኝ ስላወቅኩ ጠዋት እንድታነቢ አደረኩ፣ በህይወትሽ ውስጥ ብዙ የሚያስደስቱና የሚያስከፉ ነገሮች ተፈጥረው ያውቁ ይሆና ግን በዚህ መካከል ትልቅ ውሳኔ እንድተወስኚ የሚያደርጉ መከፋቶች አሉ፣ ዩስሪዬ አንቺን የግሌ አድርጌ እንደ ባሪያ ሳገለገልብሽ የመኖር ህልም ነበረኝ ግን አላህ አልፈቀደውም ምንያቱም ረበና የሚወዳትን ባርያው ለአመፀኛው ባርያው መስጠት ስለማይፈልግ ነው የኔ ጃድ በጣም ነው የሚወድሽ ሊነግርሽ ቢፈልግም እድሉን ግን አልሰሸጠሸውም ሁሌ የምታወሪለት ስለ አስማ ነው ያንቺ ፍላጎት ያ ቢሆንም እሱ ግን የሚወደው አንቺን ነው፡፡

☆#ክፍል_14_ይቀጥላል☆....

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

10 Oct, 19:06


☆ያያችሁት ሁሉ ለሌላው ሼር አድርጉት እስቲ እናጥለቅልቀው ፕሮፋይል እናድርገው ።😊

#ሀበሻ_ኢጅቲማዕ
❥❥нαйιƒღღ🫶

♡ ㅤ  ⎙ㅤ  ⌲        ✉️   
ˡᶦᵏᵉ    ˢᵃᵛᵉ    ˢʰᵃʳᵉ   ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ
jᵒⁱⁿ⇝
@HANIF_TUBE01

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

08 Oct, 18:05


ያው ላይኩ ባይሞላም ለቅቄዋለው በዚኛው እንደማታሳፍሩኝ ተስፋ አደርጋለሁ.....
😊

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

08 Oct, 18:04


🦋🧕እብዷ ጅልባቢስት🧕🦋

☆#ክፍል፡- 12☆

አስታውሰው ብላ የሰጠተችን ተስቢህ እሷ እንዳለችው ከሷ ጋር ብቻ ሳይሆን ከጌታዬ ጋር አቃርቦኛል፣ ዩስሪን ያሳጣኝ አንድ ነገር ቢኖር ዲኔን አለማወቄ ነው አላህን እንደ ትክክለኛ ባርያ አለመገዛቴ ነው ዩስሪን ብቻ ሳይሆን አኼራዬንም ሊያሳጣኝ የነበረውን የሚያስጠላው ማንነቴን ቀይራዋለች፣ ከሆነ ግዜ ጀምሮ ስገድ ቅራ ፁም እያለች ታስታውሰኛለች፣ በነገራችን ላይ ኢልም ብቻውን ትርጉም የለውም ኢማን ካልታከለበት ለዚህም አስታዋሽ ያስፈልጋል ምን አልባትም ዩስሪን በጃድ ልብ ውስጥ ያስገባት ወደራሱ ሊመልሰኝ ስለፈለገ ሊሆን ይችላል ስለዚህ ጌታዬን ማመፅ አልፈለግኩም ልወቅሰውም አላሰብኩም እንደውም ይበልጥ እንድቀርበው አድርጎኛል፡፡
*
ምን እየተፈጠረ እንደሆነ አላውቅም ግን የምጠይቀው ስለሌለ ዝምታን መርጫለው ኢያድ እንደ ድሮው አይደለም በጣም ቅዝቅዝ ብሏል፡፡ግን ቸኮሌት በየአይነቱ ነው የሚያመጣልኝ ጃድ ደግሞ በጣም እያወራኝ ነው የሆነ ተገላቢጦሽ ነገር ነው የሆነብኝ ነው ፣ የሚገርማችሁ ከጃድ ጋር መደዋወል እራሱ ጀምረናል ይደውልና የሚያወራው ንግግር ልብን ይገዛል፣ ትህትና የተሞላው ቁም ነገሩንና ቀልዱን እያዋዛ ነው የሚያወራው፣ በአካል ስንገናኝ ብዙም ማውራት አይፈልግሞ በስልክ ሲሆን ግን የተለየ ነው ብቻ ግን ሁለቱም ወንድማማቾች ሁሉቱም በተሰጣቸው ነገር ደስ የሚሉ ናቸው፣

ኢያድ ሰሞኑን ያመጣው የፀባይ ለውጥ ባይገባኝም፣ ብቻ ግን ከንግግሩ እንደምረዳ ወደ ሆነ ራቅ ያለ ቦታ ለመሄድ እየተዘጋጀ ያለ ሰው ነው የሚመስለው፣ ለጃድ ብዙ ግዜ ስለ አስሚ አወራዋለው ኢላሂ ብሎለት ሁለቱ ቢጋቡ ምን ያህል ደስተኛ እንደምሆን አላውቅም ለሷም በየግዜው ስለጃድ ነግሬያታለው፣ ብቻ ሁለቱን ለማቀራረብ በጣም ጥረት እያደረግኩ ነው፣

<< ኢያድ ወላሂ ስላንተ ሳላስብ የማመሽበት ምሽት የለም እየሆንክ ያለከው ነገር እየገባኝ አይደለም አንተን ላለማስጨነቅ በዬ አንስቼብህ አላውቅም ግን አሁን አልቻኩም ካንተም አልፎ እኔም የማልወደውን ዝምታ እየተላመድኩ ነው ቢያንስ የውስጥህን ሚስጥርህን ባትነግረኝም ግን በቃ የለወጠህን የቀየረህን ነገር በራሴ እንዳውቅ የሆነ ምንጭ ስጠኝ ወይ ጩኸህ ሰድበህ የሚወጣልህም ከሆነ ጩህብኝ ስደበኝና ይውጣልህ>>
ከእለታት በአንዱ ምሽት ነበር ስለሱ እያሰብኩ ያመጣውን ፀባይ ለውጥ በምን ምክንያት እንደተቀየረ ግራ ሲገባኝ የደወልኩለት
<< የኔ እብድ ቢሆንና ቢወጣልኝ ምኞቴ ነበር ግን ይሄ የማይሆን ነገር ነው በቃ ትንሽ ግዜ ብቻ ነው>>
<<ሁሌም ትንሽ ግዜ ነው ትላለህ ቆይ ልትጠፋ ነው ወይስ ከኔ ርቀህ ልትድ ነው ወይም ያጠፋሁት ጥፋት ካለ ንገረኝና ላስተካክል>>
<< የኔ እብድ አንቺ ምን ያጠፋሽው ነገር የለም ግን ህይወት ወደሽ ሳይሆን ሳትወጅ ያንቺ ገፀ ባህሪ ትቀይራለች>>
<<እሺ እንደመሰለህ ደና ደር>> ብዬ ስልኩን ዘጋሁት፣
ወላህ በጣም ከፍቶኛል አላውቅም ስለ ኢያድ ምን እንደሚሰማኝ ብቻ ግን በቃ ሲከፋው ሲደብረው ማየት አልፈልግም ብቻ አላህ ከሁላችንም በላይ አዋቂ ነው፣
*
ወንድ ልጅ ጠንካራ ነው ይባላል እኔ ግን ያጥንካሬ የተሰጠኝ አይመስለኝም በጣም ልፍስፍስ ነኝ፣ ዩስሪ አውርታኝ ስልን ከዘጋችው ቡሀላ እንባዬን መቆጣጠር አልቻኩም ቢያለቅሱት ቢያለቅሱት የማይወጣ ሲቃ፣ ሁሉም ሰው የኔ ፀባይ ለውጥ አስጨንቆታል በመለወጤ ደስተኛ ቢሆኑም ዝምታዬ ግን አስፈርቷቸዋ በተለይ ለተወሰነ ግዜ ርቄ መሄድ እንደምፈልግ ስነግራቸው የተቀበለኝ ባይኖም እኔ ግን ግዴታ እንደሆነ አሳምኛቸዋለው፣ የመሄጃ ቀኔ 1 ቀን ብቻ ነው የቀረው ……

☆#ክፍል_13_ይቀጥላል☆.....

♡❥нαйιƒ_тùве❥♡

06 Oct, 18:41


አላህ ባሮቹን ከሚያስጠነቅቅበት መንገድ ክስተቷች አንዱ የመሬት መንቀጥቀጥ ነው😞😞

}ነስዓሉ ሪዷ ረቢ ያመውላ ነስዓሉል ቀቡል ረቢ ያመውላ ወሰላመተ ሚን ኩሊ በለዓ🤲🤲🤲🤲