ሀላባ ፣ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የሃላባ ዞንን ከስልጤ ዞን ጋር የሚያስተሳስረው የአላባ-አለምገበያ-ውልባረግ መንገድ በሻሸመኔ ዲስትሪክት ከባድ የመንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል።
ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰትን የሚያስተናግደው የአላባ-አለምገበያ-ውልባረግ መንገድን ደረጃውን በጠበቀ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ለማድረግ በሻሸመኔ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከባድ የመንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል።
በስካሁኑ የስራ እንቅስቃሴ የአስፋልት ሚክስ ማምረት፣ የቤዝ ኮርስ እና አስፓልት ኮልድሚክስ ማጓጓዝ፣ 450ሜ.ኩ የአስፋልት ፕቺንግ (ኮልድሚክስ)እና የፔቭመንት ሪኮንስትራክሽን ስራዎች የተሰሩ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ክረምት ከመግባቱ አስቀድሞ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ነው።
የመንገድ ጥገናው 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲሆን ከዚህም ውስጥ ወደ 3 ኪሎ ሜትር የሚሆነው የመንገዱ ክፍል ከባድ ጥገና ተደርጎለታል። የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት ስራዎችም እየተሰራ ይገኛል።
በአሁኑ ወቅት ከ150 ሚሊዮን ብር በላይ በራስ ሀይል (ሻሸመኔ ዲስትሪክት ) የከባድ ጥገና ስራው ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ ነው።
የጥራት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተጠገነ የሚገኘው ይህ መንገድ ለረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጥ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን በመስመሩ በእጅጉ የተጎዳውን ቅድሚያ ሰጥቶ ጥገናውን በማከናወን የትራፊክ ፍሰቱን ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።
መንገዱ ካለው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው።
የመንገዱ ተጠቃሚዎች እና አሽከርካሪዎች በበኩላቸው የከባድ መንገድ ጥገና ስራው በመካሄድ ላይ መሆኑ ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቀነሱም ባሻገር በመንገዱ ብልሽት ይደርስባቸው የነበረውን የተሽከርካሪ መለዋወጫ ወጪ ከማስቀረቱም ባለፈ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በእጅጉ ያሳጥረዋል ብለዋል።
በየአካባቢዎቹ የሚመረተውን በርበሬን ጨምሮ የተለያዩ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ መሀል ከተማ በማድረስ ገበያውን በማረጋጋት አምራችና ሸማቾችን በሰፊው ተጠቃሚ ያደርጋል።
በተጨማሪም በመስመሩ የሚመላለሱ የድንጋይ ከሰል የጫኑ ተሽከርካሪዎችን በተቀላጠፈ በምቹ መንገድ ያሰቡበት ቦታ ለማድረስ ያስችላል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጎን ለጎን በበርካታ የሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚገኙትን ጉዳት የገጠማቸውን መንገዶች በራስ ሀይልና በኮንትራክትሮች የመደበኛ፣ የወቅታዊ እና የከባድ መንገድ ጥገና እያካሄደ ይገኛል ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል [email protected]
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads