መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል @zemarian Channel on Telegram

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

@zemarian


በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤት የሚከናወኑ ተግባራቶች አስመልክቶ ቆየት ያሉ ያሬዳዊ ዝማሬ በሰንበት ትምህርት ቤት ውስጥ ፣የሰንበት ት/ቤታችን ወቅታዊ ትምህርቶና የቤተክርስቲያን ወቅተዊ ጉዳዮችን ለማግኘትና ለመማማር @zemariann ይቀላቀሉን፡፡

ለማንኛውም አስተያየት @mzbot_bot

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል (Amharic)

በአማርኛ፣ ከዚህም እርስዎን ድረ-ገጽ በተግባርነት ከተወገደ የህይወት እምነት ለማቅረብ ስናንብታ፣ ለመልስምም ውስጥ ያሬዳዊ ዝማሬ በሰንበት ትምህርት ቤት ከተወገደ ነው። ለምሳሌና ለቴሌግራም ፊልሞች፣ ለመማበር ፍታዊ መረጃዎች እና ሌሎች ተጠናቋላችሁ። የህይወት እምነት ለቴሌግራም ማንኛውም ስልጣን እና ስንት፣ ስናጋር፣ ልጆቻና ሰልፍን ማጨናኛ ተጣቂዎች ለመጠቀም በመላው ተግባራት ዘገባና ትብብር አድርጉ። ለበኩላችን፣ @zemariann በሆነ ትምህርት ቤት የሚከናወኑ ተግባራቶችን ይሁኑ። ስለእርስዎ በአጭሩ መሰረታዊ መዝለስ ለመዝሙር ቆይታን እና ተጨማሪ ነገሮችን ለመተረጉ።

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

09 Feb, 17:30


የነነዌ ሰዎችም ኃጢአታቸውን አምነው (ከኃጢአቱ የሌሉበትም ቢሆን መከራው ስለማይቀርላቸው) ከመሪ እስከ ተመሪ፤ እንደ አንድ ልብ መካሪ፥ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ ሁነው፤ ንጉሡም በከተማዋ የጾም አዋጅ አስነግሮ፥ ከዙፋኑ ወርዶ፤ ሕዝቡም ማቅ ለብሰው፥ አመድ ነስንሰው፥ በፍጹም ልባቸው አዝነው አልቅሰው፥ ሕፃናት ከጡት፥ ከብቶችም ከሣር መሠማራት ተከልክለው፥ ያለምግብ በበረት ተዘግተው፤ ጾሙንም በልባዊ ጸጸት፥ ራስን ዝቅ በማድረግና በማዋረድ ንስሓ ገቡ /“የነነዌ ሰዎችም እግዚአብሔርን አመኑ” ዮናስ 3፡5 ‹‹... ለጾም ዐዋጅ ነገሩ፤ ከታላቁም ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ፡፡ ወሬውም ወደ ነነዌ ንጉሥ ደረሰ፡፡ እርሱም ከዙፋኑ ተነሥቶ መጎናጸፊያውን አወለቀ፤ ማቅም ለበሰ፤ በአመድም ላይ ተቀመጠ...” ዮናስ 3፥5-9፡፡/ እንዳለ ከአምላካችን ምሕረትን አገኙ፡፡
ነቢዩ ዮናስም ይህን አይቶ በየዋሕነቱ ‹‹እንግዲህማ ሊምራቸው ነው፣ እኔም ሐሰተኛ ነቢይ ልባል ነው›› ብሎ እያዘነና ከሕይወት ሞት ይሻላል ነፍሴን ከእኔ ውሰድ እያለ ከከተማ ወጥቶ ዳስ ሠርቶ ተቀመጠ፡፡ እግዚአብሔርም በውኑ ትቆጣ ዘንድ ይገባሃልን አለው፡፡ /ዮናስ. 4፥3-11/ አምላካችን መሐሪ በመሆኑ /አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል ፍጥረታቸውን እሱ ያውቃልና መዝ. 102፥8-14፡፡ ጥበብ 3፡፡/ ብለዋል፤ አምላካችንም /እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ በሰማይ ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን አይሰጣቸው ብሏል ማቴ. 7፥12/ ቀጥሎም ነቢዩ ዮናስ እንቅልፍ እንቅልፍ ብሎት ተኝቶ ቢነቃ ከራስጌው ቅል በቅላ ፀሐይ ስትከለክልለት አየና እጅግ ደስ አለው፡፡ ሁለተኛም ተኝቶ ቢነሣ ቅሏ ጠውልጋ፥ ደርቃ አገኘና አዘነ፡፡ እግዚአብሔርም ‹‹አንተ ላልተከልካትና ውኃ ላላጠጣሃት ቅል እንዲህ ስታዝን እኔስ በዝናም አብቅዬ፥ በፀሐይ አብስዬ ለምመግባቸው ሕዝቤ አላዝንምን?›› አለው፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር የዮናስን ፈቃዱን ይፈጽምለት (ሐሳዊ ነቢይ እንዳይሉት) ለምልክት እንዲሆን በሦስተኛው ቀን እሳት ከሰማይ ወርዶ ከፍ ከፍ ያሉትን ዕፅዋት ጫፍ ጫፋቸውን በልቶ ተመልሷል፡፡
ነቢዩ ቅዱስ ዮናስ በቀሪ ዘመኑ ፈጣሪውን እያገለገለ ኑሮ፤ በመልካም ሽምግልና በ170 ዓመት እድሜም መስከረም 25 አርፏል፡፡ ዮናስ በሕይወት ሥጋ ሣለ ሰማርያንና ነነዌን ብቻ ነበር ያስተማረው፤ ከሞተ በኋላ ግን ዛሬ ዓለምን የሚያስተምር ነቢይ ነው፡፡

ከጾሙ ረድኤት በረከት ይክፈለን፤
/በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

09 Feb, 17:30


ጾመ ነነዌ፤ ከየካቲት 3-5 (ከሰኞ-ረቡዕ)

#ነነዌ
በጤግሮስ ወንዝ ምሥራቃዊ ቆሬ፥ ከዛሬዋ የሞሱል ከተማ በተቃራኒ ከባግዳድ በሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ 350 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የነበረች ታላቅ ከተማ ነች፡፡
ነነዌን በመጀመሪያ የቆረቆራት ናምሩድ ነው፡፡ /ዘፍ. 10፥11/
በጣም ሰፊ ነበረች “የቅጥሯም ዙሪያ በእግር የሦስት ቀን መንገድ ያህል ነበረ” /ዮና. 3፥3/
እግዚአብሔር አምላካችን ነነዌን “ታላቂቱ ከተማ” በሚል ቅጽል ጠርቷል፤ /ዮናስ 3፥2፤ 4፥11/
ስለ መጥፋቷ ነቢዩ ሶፎንያስ “...ነነዌንም ባድማ እንደ በረሃም ደረቅ ያደርጋታል” በማለት ትንቢት ተናግሮባታል፡፡ /ትን. ሶፎ 2፥13/፡፡ እንደ ነቢያቱ ትንቢት ታላቋ ነነዌ ከ300 ዓመታት በኋላ ጠፍታለች፡፡
የነነዌ ሰዎች በስብከተ ዮናስ አምነው፥ ንስሐ ገብተው ድነዋል፤ በዚህም ጌታችን በወንጌል ላይ ስለ ንስሓቸውና ስለ እምነታቸው /‹‹...የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፤ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡›› በማለት አመስግኗቸዋል፡፡ ማቴ 12፥41/

#ዮናስ_ነቢየ_አሕዛብ_ወሕዝብ
ዮናስ ማለት ርግብ፥ የዋኅ ማለት ነው፡፡
በዳግማዊ ኢዮርብአም ዘመነ መንግሥት /825-784 ቅ.ል.ክ./ በሰማርያ የነበረ ነው፡፡ /2ነገሥ. 14፥25/፡፡
ቊጥሩ ከ12ቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው፡፡
ነገዱ ከነገደ ይሳኮር ወገን ሲሆን፤ #አባቱ_አማቴ_እናቱም_ሶና(የሰራፕታዋ ደግ ሴት የሆነችውና ቅዱስ ኤልያስን በዚያ በረሃብ ዘመን የመገበችው ናት)፡፡
ኤልያስ በረሃቡ ዘመን ወደ ሰራፕታዋ መበለት ቤት በመሄድ "ውኃ አጠጪኝ ጥቂት ቁራሽም አምጪልኝ" አላት፡፡ ‹‹ሕያው እግዚአብሔርን እፍኝ ዱቄት አለችኝ ጋግሬያት አንተም እኔም ልጄም (ዮናስ) በልተናት እንሞታለን›› አለችው፡፡ ኤልያስም "የረሀቡ ዘመን እስኪያልፍ ይበርክት" አላት፤ ከቤቷ ብትገባ ዱቄቱ በማድጋው፣ ዘይቱ በማሰሮው መልቶ አገኘች፡፡ ከጥቂት ጊዜም በኋላ ልጇ ዮናስ ታሞ ሞተ፡፡ እናቱም ሄዳ ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን "ሳይገባኝ ከቤቴ ገብተህ ኀጢአቴን ተመራምረህ ልጄን ትገድልብኝ?" አለችው፡፡ ነቢዩ ኤልያስም ወደ አምላኩ ሰባት ጊዜ ጸሎት አድርሶ ዮናስን ከሞተ በኋላ አስነሥቶታል፡፡
ዮናስ ትንሽ ከፍ ባለ ጊዜም ከነቢያት ጓደኞቹ አብድዩና ኤልሳዕ ጋር ሆነው የታላቁ ነቢይ የኤልያስ ደቀ መዛሙርት ሆኑ፡፡ /1ነገ.17፥1-24፤ 18፥10-24/ ነቢዩ ኤልያስ ካረገ በኋላ ደግሞ ሁሉም በተሰጣቸው አገልግሎት ተሠማርተው እግዚአቤሔርን አገለገሉ፡፡ ነቢዩ ዮናስ አርባ ዓመት ሲሞላው ሀብተ ትንቢት ተሰጥቶት ማስተማር ጀመረ፡፡
የሰማርያውን ንጉሥ ኢዮርብአምን ጠቃሚ ምክር በመለገስ የእሥራኤልን ድንበር ከሔማት እስከ ዐረብ ባሕር ድረስ እንዲይዝ አድርጎታል፡፡ /2ነገሥ. 14፥25/፡፡
ነቢዩ ዮናስ ምንም እንኳን የእስራኤል ነቢይ ቢኾንም ከምድረ እስራኤል ውጪ በነነዌ ስላስተማረ #ነቢየ አሕዛብ ወሕዝብ ይባላል፡፡ የትንቢት መጽሐፉም ዋና መልእክት እግዚአብሔር የእስራኤል ብቻ ሳይሆን የአሕዛብም አምላክ እንደሆነና በንስሐ ወደ እርሱ የተመለሱትን ሁሉ በምሕረት እንደሚጐበኝ ማሳየት ነው፡፡

#ዮናስና_ነነዌ_
የነነዌ ሰዎች ኀጢአት ከመሥፈርቱ በማለፉ፤ የእግዚአብሔር ቃል ወደ አማቴ ልጅ ወደ ዮናስ መጣ “ተነሥተህ ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ የክፋታቸውም ጩኸት ወደ ፊቴ ወጥቷልና ለእነርሱ ስበክ” አለው፤ ዮናስ ግን የፈጣሪው መሐሪነት፥ ቸርነት መስፈርት እንደሌለው ያውቃልና፤ እርሱ ቢምራቸው ማን ለቃሉና ለትንቢቱ ይገዛል፤ እኔም ሐሰተኛ ነቢይ ልባል አይደለምን? ብሎ አልሔድም አለ፤ እግዚአብሔር እየደጋገመ ሲናገረው ግን ዮናስ የዋሕ ነበረና እንዲህ የሚዘበዝበኝ ከፊቱ ብቀመጥ አይደል ብሎ ከፊቱ ለመሰወር ወደ ተርሴስ በመርከብ ኮበለለ፡፡
ዮናስ ወደ መርከብ ገብቶ ጕዞ ከተጀመረ በኋላ በእርሱ ምክንያት ታላቅ ማዕበል ተነሳ፤ በመርከቡ ውስጥ የተሣፈሩትም ሊያልቁ ሆነ፤ ሌሎች እንዲያ እየተናወጡ እርሱ ግን የእምነት ሰው፥ የዋሕና ቅን ስለሆነ ተረጋግቶ በመርከቡ ውስጥ ተኝቶ ነበር፡፡ መርከበኞቹም እጅግ ሲጨንቃቸው እያንዳንዳቸው ወደ አምላካቸው ጮሁ፤ መርከቢቱም እንድትቀልላቸው በውስጧ የነበረውን ዕቃ ሁሉ እያወጡ ወደ ባሕር ጣሉ፡፡ ባሕሩ ጸጥ ሊል ስላልቻለ ዮናስንም ቀስቅሰው “ይህ ክፉ ነገር በማን ምክንያት እንዳገኘን እናውቅ ዘንድ፤ ኑ ዕጣ እንጣጣል ተባባሉ፡፡” /ዮናስ 1፥7/፡፡ እጣ ቢጥሉ በዮናስ ላይ ወጣ፤ ዮናስም በራሱ ተጠያቂነት፤ ‹‹የእኔ ጥፋት ስለ ሆነ ወደ ማዕበሉ ጣሉኝ›› አላቸው፡፡ መርከበኞች ግን ዮናስን ለመታደግ የሚችሉትን ሁሉ አደረጉ፡፡ መርከቢቱ ወደ ምድር ትጠጋላቸው ዘንድ አብዝተው ቀዘፉ፤ የእርሱ ወደ ባሕር መጣል ፈቃደ እግዚአብሔር ስለሆነ ልፋታቸው ሁሉ ከንቱ ሆነ፡፡ ሁሉም አንድ ሆነው ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፡፡ “አቤቱ! አንተ እንደ ወደድህ አድርገሃልና ስለዚህ ሰው ነፍስ አታጥፋን፤ ንጹሕ ደምንም አታድርግብን፡፡” በማለት እያዘኑ በሐምሌ 15 ቀን ወደ ባሕሩ ጣሉት፤ ባሕሩም ከመናወጥ ጸጥ አለ፡፡
ነቢዩ ወደ ባሕር ቢጣልም የእግዚአብሔር ጥበቃ አልተለየውምና ዮናስን ይውጠው ዘንድ ታላቅ ዓሣ አንበሪን አዘዘለት፡፡ ነቢዩ ዳዊት ‹‹እግዚአብሔር የቀባውን እንዳዳነው ዛሬ ዐወቅሁ›› እንዳለ /መዝ. 19፥6/ የመረጠውን ነቢይ ለማዳን ዓሣ አንበሪን አዘጋጀለት፡፡
*ዮናስም በአሣ አንበሪ ሆድና በማዕበል ውስጥ ሆኖ ለ3 ቀናት ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ በመጽሐፍ ቅዱስም በዓሣ ሆድ ተጕዞ ያስተማረ፥ ትንቢትም የተናገረ የመጀመሪያ ነቢይ ሆነ፡፡ ዓሣ አንበሪው ዮናስን በሆዱ ቋጥሮ የሦስት ቀን ጎዳና በባሕር ውስጥ ገስግሶ በ3ኛው ቀን ነነዌ ዳር ደረቅ መሬት ላይ አራግፎ ተፋው፡፡ /ዮናስ 1፥4-16፤ 2፥1-11፣ መዝ. 138፥7-10/፡፡
ዮናስ በግዙፉ አሣ አነበሪ ውስጥም ያለ እንቅልፍ በጾም፥ በጸሎትና በምስጋና ለ3 ቀናት መቆየቱ ለክርስቶስ ትንሣኤ ምሳሌ ነው፤ ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ 3 ቀን 3 ሌሊት ኑሮ፥ ሙስና (ጥፋት) ሳያገኘው መውጣቱ አዳምና ልጆቹን ለማዳን የመጣው ጌታችንም 3 መዓልትና 3 ሌሊት በከርሠ መቃብር አድሮ ከሙታን ተለይቶ የመነሣቱ ምሳሌ ነው፡፡ ለዚህም ራሱ ጌታችን በወንጌል ‹‹ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክት ይሻል፡፡ ከነቢዩም ከዮናስ ምልክት በቀር ምልክት አይሰጠውም፡፡ ዮናስ በአሣ አንበሪ ሆድ 3 ቀንና 3 ሌሊት እንደ ነበረ፤ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ 3 ቀንና 3 ሌሊት ይኖራል፡፡ የነነዌ ሰዎች በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥተው ይፈርዱበታል፡፡ በዮናስ ስብከት ንስሐ ገብተዋልና፡፡ እነሆም ከዮናስ የሚበልጥ ከዚህ አለ፡፡›› /ማቴ. 12፥39/
**እግዚአብሔር አምላክም ለሁለተኛ ጊዜ ዮናስን ወደ ነነዌ እንዲሄድ አዘዘው፤ “ተነሥተህ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሂድ፤ የነገርሁህንም የመጀመሪያውን ስብከት ስበክላት” አለው፡፡ ዮናስም እንቀድሞው ሳያንገራግር ወደዚህች ከተማ ገብቶ እንዲህ እያለ ‹‹እስከ ሠሉስ ዕለት ትትገፈታእ ነነዌ ዐባይ ሃገር›› (እስከ ሦስት ቀን ድረስ ነነዌ ትገለበጣለች) ንስሐን ሰበከ፥ አስተማረ፡፡
@zemariian

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

07 Feb, 17:01


🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
            @zemariian

#የቤተክርስቲያን_ይትበሀል

፩) ዘመነ ክረምት
፪) መፀው
፫)  ሐጋይ


፫. ሐጋይ
ሐጋይ፦ ማለት ደረቅ ፀሐይ ማለት። እርሱም ከታኅሣሥ ፳፮ እስከ መጋቢት ፳፭ ድረስ ያለው ጊዜነው። ስለዚህ የቤተክርስቲያን ሥርዓት የሚባለው '' ወለእመ ፈቀድከ ታእምር ክፍለ ዘመኑ ለሐጋይ፣ ትወጥን አመ ፳ወ፮ ለታኅሣሥ ወትፌጽም አመ፳ ወሐሙሱ ለመጋቢት ወኁልቈ እሉ ዕለታት ተሰዓ ውእቱ ወእምዝ ኢየሐፅፅወበውስቴቶሙ ሀለዉ ንዑሳን አዝማን ፬ቱ ዘውእቶሙ ዘመነ ልደት ፤ ዘመነ ናዝሬት ፤ ዘመነ ጥምቀት ወአስተርእየ፤ ወዘመነ ጾም ዘመነ ልደት ትዌጥን አመ ፳ወተሱዑ ለታኅሣሥ ወትፌጽም እስከ አሐቲ ሰንበት።''

ዘመነ ናዝሬት ትዌጥን ድኅረ አሐቲ ሰንበት። ወበሳኒታ ሰኑይ ትዌጥን ወትፌጽም አመ ፲ ለጥር ዘውእቱ ጥምቀት ገሃድ ለእመ ኮነ ልደት በሰኑይ ፭ተ ዕለተ

በሠሉስ ለእመ ኮነ ፮ተ ዕለተ
በረቡዕ ለእመ ኮነ ፯ተ ዕለተ
በሐሙስ ለእመ ኮነ ፰ተዕለተ
በዓርብ ለእመ ኮነ ፱ተ ዕለተ
በቀዳዊት ለእመ ኮነ ፱ተ ዕለተ
በእሑድ ለእመ ኮነ ፲ተ ወ፩ደ ትረክብ ናዝሬት። ለቡ ዘንተ በተጠናቅቆ ዘመነ ጥምቀት ወአስተርእዮ ትዌጥን አመ ፲ወ፩ ለጥር ወትፌጽም አመ ፴ሁ ለጥር ወኁልቈ እሉ ዕለታት ፳ ውእቱ ዘይከውን በርዕደቱ ለጾም ለእመ የዓርግ ጾም ኃበ ላዕላይ ቀመር ዘመነ አስተርእዮ ይበጽሕ እስከ ሠሉሱ ለመጋቢት፤ ወኁልቈ ዕለታት ፶ወ፫ ውእቱ እምዝ ኢየሐፅፅ ወኢይትዌሰክ።

@zemariian
®ዲ.ን ሱራፊ

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

07 Feb, 16:15


https://youtu.be/XLmsdas7Exk

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

07 Feb, 16:15


በጾመ ፍልሰታ ዓቢይ ስብሐተ ነግህ የሚባሉ የምእራፍ ዜማዎች
በመሪ ዘምስለ ተመሪ ከነንባቡ ጋር እነሆ ብለናል
ምዕራፍ መጽሐፍ ዓቢይ ስብሐተ ነግህ ዘዘወትር ገፅ 234-236
1)ነአምን በአሀዱ አምላክ ዓራራይ
2)አቡነ ዘበሰማያት ዓራራይ

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

05 Feb, 04:32


ጥቂት ኦርቶዶክሳዊያን ባሉበት አከባቢዎች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማስቀጠል በሀገራችን የሚስተዋለው  የሰላም እጦት እንቅፋት እንደሆነበት ማኅበረ ቅዱሳን የዜማና የኪነ ጥበባት ማእከል አስታወቀ።

ጥር ፳፯/፳፻፲፯ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን የዜማና የኪነ ጥበባት ማእከል አገልጋይ ዲያቆን ዮናስ ተስፋዬ እንደገለጹት ጥቂት ኦርቶዶክሳዊያን ባሉበት አከባቢዎች የሚሰጠውን አገልግሎት ለማስቀጠል በሀገራችን የሚስተዋለው  የሰላም እጦት እንቅፋት እንደሆነባቸው ገልጸዋል።

ማኅበሩ ለበርካታ ዓመታት ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማከናወኑ የሚታወቅ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የመዝሙር ክፍል ሐዋርያዊ ጉዞዎችን በተለያዩ አከባቢዎች በተለይ ጥቂት ኦርቶዶክሳዊያን በሚገኙበት ሥፍራዎች በመንቀሳቀስ  በበርካታ  ቋንቋዎች አገልግሎቶችን በማከናወን ተደራሽ ማድረግ ችሏል።

በዚህም አገልግሎት “ወደ 54 ቋንቋዎችን በመዝሙር ተርጉመው እየሰሩ እንደሚኙ የገለጹት ዲ/ን ዮናስ አክለውም ምዕመናን በሚሰሙት ቋንቋ ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን እንዲያመሰግኑ” በሚል ዕቅድ ይዘው እየሠሩ የነበረ እንደሆነና አሁን ላይ የሀገሪቱ የሰላም እጦት አገልግሎቱን ተደራሽ እንዳያደርጉ እንቅፋት የሆነባቸውን ለመቅረፍ ማኅበሩ የተለያየ አማራጮችን እየተጠቀመ መሆኑን ገልጸዋል።

እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፍቃድ ተሰጥቷችው መንፈሳዊ ሥራዎችን እያከናወኑ የሚገኙ ማኅበራትም ወደ ገጠራማና ጠረፋማ አከባቢዎች በመሄድ እግዚአብሔርን የሚያገለግሉ ምእመናንን የማስተማርና የማገልገል ሥራዎችን  መስራት ቢችሉ  በማለት ዲ/ን ዮናስ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

04 Feb, 11:24


ማኅበረ ቅዱሳን በወላይታ ማእከል  የበገና ሠልጣኞችን አስመረቀ።

ጥር ፳፮/፳፻፲፯ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን በወላይታ ማእከል ፋይናንስና ልማት ተቋም ለ፱ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 34 የበገና ሠልጣኞች በወላይታ ሶዶ ኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ጥር ፳፭/፳፻፲፯ ዓ.ም አስመርቋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ የደብሩ ዋና አስተዳዳር መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ወልደ አማኑኤል ጃተና፣ አባቶች፣ የሠልጣኝ ቤተሰቦችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች የተገኙ ሲሆን በልዩ ልዩ ቅኝቶች የተሰናዱ የበገና መዝሙራት በተመራቂዎችና ሌሎች መንፈሳዊ ዝግጅቶች ቀርበዋል።

በመጨረሻም ለሠልጣኞች በማኅበረ ቅዱሳን የተዘጋጀ የምስክር ወረቀትም ተሰጥቷል።

መዝሙረ ማኅሌት ቁ፩ ¶ቻናል

04 Feb, 11:24


“ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለምን የአዋልድ መጻሕፍትን ትጠቀማለች” በሚል መሪ ቃል የቦሩ ሜዳ  መርሐ ግብር መከናወኑ ተገለጸ።

ጥር ፳፯/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን ወርኃዊ የስብከተ ወንጌል ጉባኤ  “ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለምን የአዋልድ መጻሕፍትን ትጠቀማለች” በሚል መሪ ቃል የቦሩ ሜዳ የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር ከልዩ ልዩ ቤተ እምነቶች የተውጣጡ ተሳታፊዎች በተገኙበት በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ  ውስጥ ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም ተካሂዷል።

በዕለቱ የአዋልድ መጻሕፍት መነሻ እና መድርሻ ከየት ወዴት እንደሆነ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ምላሽ የተሰጠ ሲሆን ከታዳሚዎችም ለተነሡ ጥያቄዎች በመምህር ባሕረ ጥበባት ሙጩ እና በመምህር  ዮሐንስ ጌታቸው ማብራሪያ ተሰጥቷል።

የመርሐ ግብሩ ተሳታፊዎች በዕለቱ አጀንዳ ላይ  የፈለጉትን ጥያቄ ፊት ለፊት የሚያቀርቡበት እና ምላሽ የሚያገኙበት ቦሩ ሜዳ የተባለ መርሐ ግብር በማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ በየሦስት ወሩ የሚካሄድ መሆኑ ይታወቃል።

14,414

subscribers

2,119

photos

87

videos