EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን @ethiopianfoodanddrugauthority Channel on Telegram

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

@ethiopianfoodanddrugauthority


ETHIOPIAN FOOD AND DRUG AUTHORITY /EFDA/
This is EFDA'S official Telegram Channel
For more updates please visit
Free call 8482
join the Channel
t.me/ethiopianfoodanddrugauthority

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን (Amharic)

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት እናዳስሙን መፅሀፍ በነፃነት ለማገናኘት እና በጥናት ለመቀላቀል የEFDA የአስተዳደር ቴሌግራም ቦታ ነው። የተጨማሪ ቁጥር 8482 በነጻ እንደገና ይላኩልን። በተጨማሪ ርዕሰ መረጃዎች ለመረዳት እባኮንናይድ ትልቅ ቤቶች ይላኩልን። t.me/ethiopianfoodanddrugauthority የላብራቶሪ የምግብና መድኃኒት እቃውዝባን።

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

14 Feb, 14:50


የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወር ዕቅድ አፈፃጸም በዋና ዋና መለኪያዎች ሲመዘን አበረታች ውጤት መመዝገቡ ተገለፀ፡፡

የካቲት 7/2017 ዓ.ም በአዳማ ከተማ የባለስልጣኑ የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ አመት የዕቅድ አፈፃጸም ግምገማ መድረክ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ሲከፍቱ እንደተናገሩት የሚካሄደው ግምገማ ዋና ዓላማ የባለስልጣኑ 15 የትኩረት አቅጣጫዎች ከውጤት እና ከተገኙ በጎ ተፅህኖዎች አንፃር በጥልቀት ተገምግሟል።

የጥራት ስራን ባህል ማድረግ እንደሚገባ እንዲሁም ለማቹሪቲ ሌቭል ስሪ የተሰሩ ስራዎች ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ዋና ዳይሬክተሯ ያሳሰቡ ሲሆን በተለይ ስራዎች በዕቅድ ተመስርቶ እየተገመገመ መሰራት ዋነኛ ትኩረታችን መሆን እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡

የቅኝትና የቁጥጥር ስራችን የተቀናጀ ሊሆን ይገባል ያሉት ዋና ዳይሬክተሯ በሕገወጥ የወባ መድኃኒቶች ቁጥጥር ዙሪያ የተሰሩ ስራዎች መልካም መሆኑን ገልፀው የትምባሆ ስራ ከክልሎች ጋር ተቀናጅቶ በመስራት ረገድ መጠናከር እንዳለበትና ስራዎችን አረጋግጦ ከመመዘን አንፃር እያንዳንዱ የስራ ኃላፊ በትኩረት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

በግምገማ መድረኩ የ2017 በጀት ዓመት የግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም በስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈፃሚ በፋይዛ አባቢያ የቀረበ ሲሆን ህብረተሰቡን የቁጥጥር ባለቤት ለማድረግ ፣ቅልጥፍናና ውጤታማነትን ለማሻሻል፣ የምግብ ደህንነት ቁጥጥርን ለማጠናከር፣ የመድኃኒት ደህንነት፣ጥራት፣ፈዋሽነት እና አግባባዊ አጠቃቀም ቁጥጥርን ለማሻሻል በተቀመጡ 15 የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የተከናወኑ ተግባራት በዋና ዋና መለኪያዎች ሲመዘኑ አበረታች ውጤት ተገኝቷል፡፡

በተጨማሪ የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያና የመልካም አስተዳደር አፈፃጸም ላይ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡  

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

14 Feb, 06:19


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣንና ኢምፓወር ስዊስ ሳርል የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራረሙ

የካቲት 6/2017 አዲስ አበባ፡- በፊርማው ስነስርዓት ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ በአፍሪካ ውስጥ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እየሰራ መሆኑን ገልፀዋል። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የቀጠናው የስልጠና ማዕከል ለመሆንም በርካታ የሪፎርም ስራዎች እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው  በሐገሪቱ ከሚገኙ 12 ክልሎች እና ሁለት ከተማ መስተዳደሮች ስር ከሚገኙ ተቆጣጣሪ አካላት ጋር በመቀናጀት ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡ ኢምፓወር ስዊስ ሳር መግባቢያ ሰነዱ እንዲዘጋጅ ለሰሩት ስራ እንዲሁም የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስምምነቱን እንዲፈረም ላደረጉት አስተዋፅኦ አመስግነዋል። 

የኢምፓወር ስዊስ ሳርል ዳይሬክተር እና መስራች ፕሮፌሰር ፖል ላልቫኒ በበኩላቸው ከስድስት ወራት በፊት ወደ ኢትዮጵያ በመመጣት የባለስልጣን መስሪያ ቤቱን ፍላጎቶች ማጥናታቸውን የገለፁ ሲሆን ይህ ስምምነት ለባለስልጣኑ እና ኢምፓወር ስዊስ ሳርል ብቻ ሳይሆን ከተቋማት የዘለለ ጥቅም እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ ይህ ትብብር ለሁለቱም ወገኖች ጥቅም እንደሚያስገኝ እምነታቸው መሆኑን አስታውቀዋል። 

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርን የወክሉት ወ/ሮ ሃይማኖት አበራ ሚኒስቴሩ በዘርፉ የሀገሪቱን ፍላጎቶች በተገቢው ሁኔታ ለማሟላት ከባለስልጣኑ ጋር በትብብር ለመስራት ያለውን ቁርጠኝነት ተናግረዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

03 Feb, 12:16


ማቹሪቲ ሌቭል ሶስት ለማሳካት ሁሉም ሠራተኛ የበኩሉን ሚና መወጣት አንዳለበት ተገለጻ፡፡
ጥር 26/2017 አ/አ፡ ባለስልጣኑ ለሰራተኞቹ ማቹሪቲ ሌቭል ሶስት ለማሳካት እየተካሄደ ያለውን የኦዲትዝግጅት እና የተሰሩ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ለሠራተኞቹ ግንዛቤ ሰጥቷል፡፡
በግንዛቤ መድረኩ መክፋቻው ላይ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ደይሬክተር ወሪ/ት ሄራን ገርባ እንደተናገሩት ማቹሪት ሌቭል ሶስት በአለም ጤና ድርጅት ቤንች ማርኪንግ መሰረት በዓለም ዓቀፍ በተዘጋጁ የዎዲት መስፈርቶች መሰረት በመመዘን የሀገራት የመድኃኒት ጥራት ቁጥጥር ኦዲት በማድረግ የተቆጣጣሪዎችን የቁጥጥር ደረጃ የሚበየንበት መሆኑን በመግለጽ እንዚህን ደረጃዎች በማሟላት መቻል እንደ ሀገር ለጤና ግብዓት ቁጥጥር ዘርፍም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳው የላቀ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ዋና ዳይሬክተሯ እንደተናገሩት እንደዜጋ ሀገራችንና ህዝባችንን ለማገልገል የተሰጠን ዕድል በመጠቀም የሀገራችን የመድኃኒት ቁጥጥር ዘርፍ ማቹሪቲ ሌቭል ሶስት ኦዲትን በማሳካት የውጭ ሀገራት ምርቶች እየተቀበልን የምንኖርበት ዘመን እንዲያበቃና በሀገሪቱ የሚገኙ የመድኃኒት አምራቾችን ቁጥር ለመጨመር ለሌሎች ሀገራትም የሚሆኑ የመድኃኒት ምርቶች ለማምረት በር ከፋች በመሆኑ የአለም የጤና ድርጅት ማቹሪቲ ደረጃ ሶስት ኦዲትን በስኬት ማጠናቀቅ እንደሚገባ ገልፀዋል። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱን ለኦዲቱ ብቁ ለማድረግ የህግ ማሻሻያዎች መደረጉን ጭምር አስታውቀዋል።
እስከ አሁን በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ለሰራተኞቹ ማብራሪያ የሰጡት የጥራት ስራ አማራር መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ አወት ገ/እግዚአብሄር ግምገማውን በስኬት ለማጠናቀቅ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን የገለፁ ሲሆን የባለስልጣኑ ሰራተኞች ከመደበኛ የስራ ሰዓት ውጪ ተጨማሪ ስራዎችን ለመስራት ቁርጠኝነታቸውን ገልጸዋል።

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

01 Feb, 10:32


የአገሪቱን የመድኃኒት የቁጥጥር ስርዓት ለመገምገም የዓለም ጤና ድርጅት ለሚያደርገው የመጨረሻ የኦዲቲንግ ስራ ተገቢ የማስተካከያ ስራዎች በትኩረት እየተሰሩ እንደሚገኙ ተገለፀ፡፡

ጥር 24/2017 ዓ.ም አዳማ ከተማ በተዘጋጀው የግምገማ መድረክ ላይ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ እንደተናገሩት ሰኔ 13/ 2015 ከተካሄደው የመጀመሪያ ኦዲት በኃላ ተቋማዊ የልማት ዕቅድ በማዘጋጀት እንደ ቁጥጥር ዘርፉ መስተካከል ያለባቸውን ዶክሜንቶችና ሌሎች ጉዳዮች በማስተካከል ለሁለተኛ ዙር የኦዲቲን ስራ አስፈላጊው ዝግጅቶች ተደርጓል፡፡

እንደ አገር የመድኃኒት ቁጥጥር ስርዓቱ በመገምገም ማቹሪቲ ሌቭል ስሪ ለማግኘት ባለስልጣኑ ከራሱ የስራ ክፍሎች በተጨማሪ ባለሙያዎችን የክልል ተቆጣጣሪ አካላት ድረስ በመላክ እስከ አራት የሚደርሱ ድጋፋዊ ክትትሎች ማድረጉን ዋና ዳይሬክተሯ ጠቁመዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም የአራተኛው የድጋፋዊ ክትትሉ ያለበት ደረጃን በመገምገም የዓለም ጤና ድርጀት ለሚያደርገው የመጨረሻ ኦዲት የሚያበቁ የማስተካከያ ስራዎች በሁለት ቀናት ውስጥ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ዋና ዳይሬከተሯ አብራርተዋል፡፡

በዚህ የግምገማ መድረክ ላይ የባለስልጣኑ የመድኃኒት ዘርፍ እና ጉዳዮች የሚመለከታቸው የስራ ክፍሎች እንዲሁም የሁሉም ክልሎችና የሁለቱ የከተማ አስተዳደር የጤና ግብዓት ተቆጣጣሪ አካላት ኃላፊዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

29 Jan, 14:00


የባዮኢኩቫለንስ ጥናት ፍኖተ ካርታ ትግበራ በጥሩ መግባባት ላይ ተመሥርቶ እየተሠራ እንደሚገኝ ተገለፀ
ጥር 21/2017 በተካሄደው አውደ ጥናት በአገር ውስጥ የሚመረቱ መድኃኒቶች ንፅፅራዊ የፈዋሽነት ደረጃን የሚፈትሸው የባዮኢኩቫለንስ ጥናት ፍኖተ ካርታ ትግበራ ተገምግሟል፡፡
የባዮኢኩቫለንስ ጥናት ፍኖተ ካርታ ትግበራ ደረጃ ክትትልና ግምገማ በየወሩ በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከጤና ሚኒስቴርና ከአርማወር ሐንሰን የምርምር ተቋም በተወከሉ ባለሙያዎች በጋር የሚያካሂድ ነው፡፡
የመድሃኒቶች ባዮኢኩቫላንስ ጥናት በእንክብል መልክ ተዘጋጀተው በአፍ የሚወሰዱ መድኒሃቶች ባበለስልጣን መስሪያ ቤቱ የገበያ ፈቃድ ለማግኘት ከሚያስፈልጉ መሰራታዊ መስፈርቶች አንዱ መሆኑንና ከዚህ ቀድም ከውጭ ሀገር በሚገቡ መድኃኒቶች ላይ ብቻ ተግባራዊ ሲሆን የነበረ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ፍኖተ ካርታው ከተዘጋጀ ወዲህ ደረጃ በደረጃ በአገር ውሰጥ ለሚመረቱ መድኃኒቶች ጭምር ጥናቱ መካሄድ እንደለበት ከዓለም ጤና ድርጅት በቀረበው ሀሳብ መሰረት የባዮኢኩቫለንሱ ፍኖተ ካርታ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባቱ ታውቋል፡፡
የፍኖተ ካርታው መዘጋጀት የመድሃቶችን ፈዋሽነት በአስተማማኝ ሁኔታ የሚያረጋግጥ፣ የአገር ውስጥ የመድኃኒት አምራቾችን አቅም የሚገነባ፣ ምርቶቻቸውን ከአገር ውጭ ለመላክ ዕድል የሚፍጥርና አጋርነትና ትብብርን በዘርፉ የሚፈጥር ነው፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

28 Jan, 12:41


በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት በላስልጣን እና በኢትዮጵያ ፋርማሲስቶች እና የፋርማሲቲካል ሳይንቲስቶች ማህበር በዲያስፖራ (EPPAD) መካከል በጋራ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ፡፡

ጥር/20/2017 አዲስ አበባ፡ ባለስልጣኑ መቀመጫውን በቨርጂንያ አሜሪካን ካደረገው የትውልደ ኢትዮጵያውያን የመድኃኒት ባለሙያዎችና ሳይንቲስቶች ማህበር (EPPAD) ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል፡፡
በፊርማ ስነ-ስርዓቱ ወቅት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሔራን ገርባ እንደተናገሩት ባለስልጣኑ የአፍሪካ የልህቀት ማዕከል ለመሆን እያደረገ ባለው ጥረት ማህበሩ ከዚህ ቀደም የቁሳቁስ ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው ተቋሙ ፋርማሲስቶች እና የፋርማሲቲካል ሳይንቲስቶች ማህበር አባላት ያላቸውን አቅም ፣ውቀትና ልምድ በሀገር ውስጥ የቁጥጥር ዘርፉን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ቴክኒካዊ ድጋፍ እንዲያደርጉ እድል የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡
ባለስልጣኑ ከሙያ ማህበሩ ጋር የስምምነት ሰነዱ በተፈረመበት ወቅት ባለስልጣኑ የአለም ጤና ድርጅት ማቹሪቲ ሌቭል 3 ቤንችማርክ ለመደረግ ዝግጅት እያደረገ ባለበት ወቅት መሆኑ መልካም አጋጣሚ መሆኑን በማስረዳት በቀጣይ የምግብና የጤና ግብዓት ቁጥጥር ከታች እስከ ላይ ለማጠናከር በሚሰራው ስራ የማህበሩ አባለት የካበተ እውቀትና ልምድ ሀገር ውስጥ ለሚገኙ ባለሙዎች በማካፈል ሚናቸውን እንዲወጡ ስምምነቱ በር ከፋች መሆኑ አስታውቀዋል፡፡
የማህበሩ የሬጉላቶሪ ቡድን መሪ የሆኑት ዶ/ር አሌክስ አካሉ በበኩላቸው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ትውልደ ኢትዮጵያውያን ሐገራቸውን በሙያቸው እንዲያግዙ ላመቻቸው እድል አመስግነው በጋራ መግባቢያ ሰነዱ መሰረት ድጋፍ ማድረግ በሚቻልበት መንገድ ንግግር አድርገዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

27 Jan, 12:21


በስጋት ተኮር የድህረ ገበያ ጥናት ላይ በተገኙ ውጤቶች ዙሪያ አውደ ጥናት ተካሄደ

የኢትዮጵያ የምግብና የመድኃኒት ቁጥጥር ባለሥልጣን በፋርማኮቪጂላንስ እና ክሊኒካዊ ሙከራዎች ዙሪያ በአውሮፓውያኑ 2024 ዓ.ም ያካሄዳቸውን እንቅስቃሴዎች ለመገምገምና ለመወያየት አውደ ጥናት አካሂዷል። የአውደ ጥናቱ ዋና ትኩረት በስጋት ተኮር የድህረ ገበያ ጥናት የናሙና መሰብሰብ መርሆዎች፣ ቁጥጥር እርምጃዎች እና የላቦራቶሪ ምርመራ ውጤቶች ላይ ነበር።

አውደ ጥናቱን በይፋ የከፈቱት የባለስልጣኑ የመድኃኒት ደህንነት ክትትል እና የህክምና ሙከራ መሪ ስራ አስፈጻሚ አስናቀች አለሙ ሲሆኑ በኢትዮጵያ የመድኃኒት ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ ስጋት ተኮር የድህረ ገበያ ጥናት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አስረደረድተዋል ።

ከ2016 ሁለተኛ ግማሽ ዓመት ጀምሮ እስከ 2017 የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ስጋት ተኮር መሰረት ባደረገ መልኩ የተሰሩ  የድህረ ገበያ ጥናት በዝርዝር የቀረቡ ሲሆን የተሰበሰቡ ናሙናዎች ላይ በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ  ከባለስልጣኑና ከክልሎች ተወክለው በተገኙ ውይይት ተደርጓል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

27 Jan, 09:22


https://shorturl.at/VDO4g

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

21 Jan, 09:35


የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱን ጎበኙ

ጥር 13/2017 አዲስ አበባ፡ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጄ ዱጉማ በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በመገኘት የባለስልጣኑን የስራ እንቅስቃሴ ጉብኝት ያደረጉ ሲሆን በጉብኝቱ ወቅት እንደገለጹት በኢትዮጵያ ውስጥ ጥራት ያለው፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና ውጤታማ የሆነ የምግብና የጤና ግብዓት ምርቶች እንዲደርሱ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቀው ምርቶች ወደ ገበያ ከመግባታቸው በፊት ጥራታቸውን በጥብቅ በመፈተሽና በመቆጣጠር ዙሪያ እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናከሮ እንዲቀጥል በመግለጽ በቀጣይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

በጉብኝታቸው ወቅት የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎች ላብራቶሪ እንዲሁም የተለያዩ የስራ ክፍሎች እየሰሩ ያሉትን ስራዎች በአካል ተገኝተው የተመለከቱ ሲሆን በወቅቱ ከነበሩ ደንበኞች ጋርም ስለባለስልጣን መስሪያ ቤት አገልግሎት አሰጣጥ አስተያየቶችን የጠየቁ ሲሆን በቀጣይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ባለስልጣኑ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ እንዲያስቀጥል  በሚያስችልበት ሁኔታ ላይ ድጋፍ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

05 Jan, 18:20


https://youtu.be/SFHPFiY5PFs

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

04 Jan, 08:48


የህክምና መሳሪያ ደህንነት ጥራትና ውጤታማነት ጉድለቶችን በተቀናጀ መልኩ ሪፖርት ማድረግ የቁጥጥር ስራን እንደሚያሳልጥ ተገለፀ ፡፡

ታህሳስ 25/2ዐ17 ዓ.ም አዳማ፡- የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን የህክምና መሳሪያ ደህንነት፣ ጥራትና ውጤታማነት  ቁጥጥር ሪፖርት አደራረግ ላይ ከአዲስ አበባ ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል፡፡
ስልጠናውን የከፈቱት  በባለስልጣኑ የህክምና መሣሪያዎች ም/ዋና ዳይሬክተር  ዶ/ር ሻርማርኬ ሸሪፍ እንደተናገሩት ተቋማችን የህክምና መሣሪያዎች ወደ ሃገር ሲገቡ የደህንነት፣ ጥራትና ውጤታማነት ቁጥጥር ያደርግባቸዋል፡፡ሆኖም በአገልግሎት ላይ በሚውሉበት ጊዜ የተለያዩ የጎንዮሽ ጉዳት ይኖራቸዋል፡፡ ይህንን የጎንዮሽ ጉዳት በየደረጃው ያሉ የጤና ባለሙያዎች ሪፖርት ካላደረጉ ማወቅ አይቻልም፡፡ በመሆኑም የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ መናበብ እና በጋራ መስራት ስለሚያስፈልግ ስልጠናውን በተግባር ላይ እንዲያውሉ አደራ  ብለዋል፡፡ 

ስለ ስልጠናው ያብራሩት የባለስልጣኑ የህክምና መሣሪያ አምራች ኢንስፔክሽን መሪ ስራ አስፈፃሚ አቶ ሚኪያስ ጴጥሮስ እንደተናገሩት የህክምና መሣሪያ ደህንነት፣ ጥራትና ውጤታማነት  ቁጥጥር  በአገራችን ያልተጠናከረና ያልተደራጀ መሆኑን ጠቁመው ከዚያው ጐን ለጐን በባለሙያዎችም እንከኖች ሲገኙ ሪፖርት ማድረግ ያልተለመደ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

የጤና ግብአት ቁጥጥሩን ለማዘመንና የህብረተሰባችንን ጤና ለማስጠበቅ የተደራጀና የተቀናጀ የህክምና መሣሪያ ደህንነት ጥራትና ውጤታማነት  ጉድለት ሪፖርት ማድረግን እንደ ሃገር መተግበር የዚህ ስልጠና ዋና አላማ እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

01 Jan, 19:50


ከአግሮ ፕሮሰሲንግ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ጋር  አብሮ መስራት የምግብ  ጥራትንና ደህንነትን  ለማስጠበቅ  ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ፡፡

ታሃሳስ 23/2017 አዲስ አበባ፦  የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን  ከኦሮሚያ  ኢንዱስትሪ ፓርክ የልማት ኮርፖሬሸ(OIPDC)ን ጋር የምግብ  ጥራትንና ደህንነትን  ለማስጠበቅ የጋራ መግባብያ ሰነድ ተፈራረሙ፡፡ በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሔራን ገርባ እንደተናገሩት የምግብ ጥራትና ደህንነት ማስጠበቅ ዋና ተግባራችን  እንደመሆኑ  ተቋማችን የምግብ አግሮ ኢንቨስትመንቶች ከመሰረቱ ጀምሮ የተሻለ ደህንነትና ጥራት ኖሯቸው ምርታቸውን እንዲያመርቱና  ለገበያ እንዲያቀርቡ እንደግፋቸዋለን፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ኢንቨስተሮች መዋለ-ንዋያቸውን በምግብ አግሮ-ፕሮሰስ ላይ እንደያፈሱ  በማበራታታት የማሰተናገድ አቅማችን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደግን  ለአገር ኢኮኖሚ ዕድገት የበኩላችንን  እያተወጣን  አንገኛለን ያሉ ሲሆን ፊርማውም ከወረቀት አልፎ ተግባራዊ  ይሆናል ሲሉ ተነግረው ሁሉም የአግሮ ፕሮሰሲንግ ፓርኮች የምግብ ጥራት ምርመራ ላብራቶሪ እንዲያደረጁ ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል፡፡

የኦሮሚያ አግሮ ፕሮሰሲንግ እንዱስትሪ ፓርክ ምክትል ስራ አሰኪያጅ አቶ መንግስቱ ረጋሳ  በበኩላቸው  ከኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ጋር  ለመስራት በመፈራራማችን  ለስራችን መቃናት ግማሽ መንገድ  የተጓዝን ያህል ይሰማናል ያሉ ሲሆን ከህዳሴ ግድብ በመቀጠል ብዙ  ገንዘብ  የሚፈስበት ዘርፍ ኢንዱስተሪ ፓርክ  ነው ያሉት ምክትል ስራ አስኪያጁ የባለሀብቶች ጥያቄ ላመረቱት የምግብ  ምርት የገበያ ፈቃድ ማግኘት ነው፤ በመሆኑም ከተቋሙ ጋር ስንሰራ  የምግብ ጥራትና ደህንነትን  በማስጠበቅ ሁሉንም ባለድርሻ አከላት ተጠቃሚ እናደርገለን ሲሉ ተነግረዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

01 Jan, 19:46


ኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ከUSPQM ፕላስ ጋር በመተባበር ከክልል ተቆጣጣሪ አካላት ጋር የአንድ ቀን አውደ ጥናት አካሄደ።

የዚህ የምክክር አውደ ጥናት የክልል ተቆጣጣሪ አካላት ከታንዛኒያ እና ዚምባብዌ ተቆጣጣሪ ባለስልጣናት ጋር በተደረገው የልምድ ልውውጥ ውጤት ላይ ለመወያየት እና የጥራት አስተዳደርን በክልል ተቆጣጣሪ አካላት ውስጥ ተግባራዊ ለማድረግ እቅድ የነበረውና በ2025 የመጀመሪያ ወራት ውስጥ በአለም ጤና ድርጅት ለማቹሪቲ ሌቭል ሶስት ይፋዊ የቤንችማርኪንግ ግምገማ ዝግጅት በመገምገም በክልል ተቆጣጣሪዎች በኩል የተገኘውን ልምድ በመቀር ቀሪ ስራዎችን  ለማጠናቀቅ የሚያግዝ መሆኑ ተገልጿል።

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

31 Dec, 14:53


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 የአቅመ ደካማ ነዋሪ ቤት አድሶ አስረከበ
ታህሣሥ 22/2017 ቀን  ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመበት ዓላማ በተጨማሪ ማህበራዊ ግዴታን ለማገዝ በርካታ የበጎ አድራጎት ስራዎችን ሲሰራ የከረመው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የዚሁ ስራ አንድ አካል የሆነው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 የሚገኝን ቤት በማደስ ለባለቤቱ አስረክቧል
በቤት ርክክቡ ወቅት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሔራን ገርባ እንደተናገሩት ይህ ቤት በ2 ወራት ውስጥ ታድሶ ለነዋሪዋ ወይዘሮ ስንታየሁ ባህሩ ለማስረከብ ባለስልጣኑ ከግርማ ገብረስላሴ ህንፃ ተቋራጭና ከወረዳው ስራ አስፈፃሚ ተቀራርቦ ሲሰራ መክረሙን ገልፀዋል፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ መንግስት በአዋጅ ከሰጠው መንግስታዊ ኃላፊነት ጎን ለጎን ማህበረሰቡን ለመደገፍ በቂርቆስ ወረዳ 02  ለሚገኙ ተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ፣ በጋሞ ጎፋ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎች፣ ለመከላከያ ሠራዊት የመድኃኒትና የህክምና መሳሪያዎች ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው የባለስልጣኑ ሠራተኞችና አመራሮች ከደመወዛቸው ተቆራጭ በማድረግ የሚያደርጉት ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል  ጠቁመው ታድሶ ለመኖሪያነት ምቹ የሆነውን ቤት ለወይዘሮ ስንታየሁ ባህሩ በዛሬው ዕለት አስረክበዋል፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ስራ አስፈፃሚ አቶ አበራ አለሙ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በየጊዜው በወረዳው የሚገኙ ነዋሪዎችን ለመደገፍ እየሰራ ያለው ስራ ለሌሎች ተቋማትም ምሳሌ እንደሚሆን ተናግረው ቤቱ በዚህ ደረጃ ታድሶ ለነዋሪዋ በመሰጠቱ በስራው የተሳተፉትን ሁሉ ያመሰገኑ ሲሆን ቤቱን በተገቢው ጥራት አድሰው ለዚህ ያበቁት ግርማ ገብረስላሴ ህንፃ ተቋራጭን በራሳቸውና በሚመሩት ወረዳ ስም አመስግነዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

05 Dec, 16:15


አገር አቀፍ የትምባሆ ቁጥጥር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ወደ ክልል ወርደው የተሰሩ የትምባሆ ቁጥጥር ስራዎችን የመገምገም ተግባር ቀጣይነት ባለው መልኩ መስራት እንዳለባቸው ተገለፀ፡
ህዳር 26/2017 ዓ.ም ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አገር አቀፍ የትምባሆ ቁጥጥር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላትን እንደገና ለማደራጀትና በቀጣይ ሊሰሩ ስለታቀዱ ስራዎች ለተለያዩ የፌደራል የመንግስትና መንግስታዊ ያልሆኑ ባለድርሻ አካላት የአስተዋወቀበትን መድረክ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ሲከፍቱ እንደተናገሩት አገር አቀፍ የትምባሆ ቁጥጥር አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት በጋራ የሚሰሩ የትምባሆ ቁጥጥር ስራዎችን ክልል ድረስ ወርደው መጎብኘት እንዳለባቸው ጠቁመው ይህም ትኩረት ተሰጥቶ በቀጣይነት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የመንግስት ተቋማት በተለያዩ አደረጃጀቶች ምክንያት በመቀያየራቸውና ሰራተኞችም በተለያየ ምክንያት ስራቸውን ሲቀይሩ ከአስተባባሪ ኮሚቴው ሲወጡ በመቆየታቸው እንደገና ኮሚቴውን አዋቅሮና አጠናክሮ ማስቀጠል በማስፈለጉ መደረኩ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡
በቀጣይነት ኮሚቴው በጋራ በሚሰሩ ስራዎች ላይ መግባባት በመፍጠር አባላቱ ከባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ጋር በተናጥል የጋራ መግባቢያ ሰነድ እንደሚፈራረሙ እንደሚጠበቅ ከመድረኩ ለማወቅ ተችሏል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

04 Dec, 15:20


ዓለም አቀፉ የአካል ጉዳተኞችና የነጭ ሪባን
ቀን ተከበረ


በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ32ኛ ጊዜ የሚከበረውን የአካል ጉዳተኞች ቀንን እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ19ኛ ጊዜ እየተከበረ የሚገኘውን የፀረ ፆታዊ ጥቃት ቀን ክብረ በዓልን ለማክበር በተዘጋጀው የፓናል ውይይት ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ወይዘሮ ውብናት ቢራራ እንደተናገሩት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ለሴቶችና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ለማድረግ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን በመግለፅ ሴቶች ነፃ የጡት ካንሰር ምርመራ እንዲያደርጉ እድሎች መመቻቸታቸውን ያስታወቁ ሲሆን በስራ ገበታ ላይ የሚፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችን ለመጠቆም የሚያስችል በቴክኖሎጂ የታገዘ ስርዓት እየተዘረጋ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ከጤና ሚኒስቴር የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ የተገኙት አቶ እናውጋው አለማየሁ በበኩላቸው በዓለማችን ላይ ከሚገኙት አካል ጉዳተኞች መካከል 80 ከመቶ የሚሆኑት በታዳጊ ሐገራት እንደሚገኙ ገልፀው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የጤናውን ሴክተር መሠረተ ልማት ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ውይይቱ ከሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አካቶ ትግበራ ስራ አስፈፃሚ ባለሙያ ወይዘሮ እቴነሽ ነመራ ባቀረቡት ፅሁፍና የጉድ ላክ የሱስ ማገገሚያና የስልጠና ማዕከል መስራችና ባለራዕይ አቶ ዮናታን ሊዮን በህይወት ልምዳቸው ዙሪያ አስተማሪ ንግግር በማድረግ በድምቀት ተከብሯል

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

02 Dec, 13:05


የመድኃኒት ደህንነትና ውጤታማነት ለማስጠበቅ በስራ ላይ ካሉ ስልቶች በተጨማሪ የመድኃኒት ምርት ስርጭት ክትትል ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ እንዲውል ባሉ ነባራው ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደረገ ፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሄራን ገርባ ሜዲካል ቫሊዩ ቼን (MVC) ከተሰኘ የባህሬ የመድኃኒት ስርጭት ክትትል ቴክኖሎጂ አቅራቢ ድርጅት ጋር የቁጥጥር ስራውን ለመጀመር የድርጅቱ የልዑካን ቡድን አባላት ጋር በአደረጉት ውይይት እንደተናገሩት ይህ ፕሮጀክት መንግስት ከግሉ ሴክተር ጋር በትብብር ለመስራት ያለውን ፍላጎትና ቁርጠኝነት አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመው በባለስልጣኑ በኩል ምንም አይነት ወጪ እንደማይኖርና ወጪውም የቴክኖሎጂ አቅራቢው ከመድኃኒት አምራች ድርጅቶች ጋር በሚያደርገው ስምምነት የሚሸፈን መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በወቅቱም ከድርጅቱ ኃላፊ ጋር ሌሎች ዝርዝር ስምምነቶችን ተፈራርመዋል፡፡
የሜዲካል ቫሊዩ ቼን ድርጅት ኃላፊ ሼካ ዲያ ቢንት ኢብራሂም አል ካሊፋ በበኩላቸው ድርጅታቸው የሚያቀርበው ቴክኖሎጂ ባህሬን ውስጥ ለውጥ ማምጣቱን ገልፀው የምንስራው ለአንድ ግብ ነው ይህም የታካሚዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ከደረጃ በታች የሆኑና ሀሰተኛ መድኃኒቶች መከላከል ዋነኛ ተግባራችን ነው ካሉ በኃላ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱም ድርጅታቸው አብሮ እንዲሰራ በመፍቀዱ አመስግነዋል፡፡
የቫሊዩ ቼን ልዑካን ቡድን አባላት በአገር ውስጥ በሚኖራቸው ቆይታ የአገር ውስጥ የመድኃኒት ፋብሪካዎችን የሚጎበኙ ሲሆን ባለስልጣን መስሪያ ቤቱም ከድርጅቱ ጋር በጋራ ለመስራት ከወራቶች በፊት የመግባቢያ ስምምነት ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ወኪሉ በኩል መፈራረሙ ይታወሳል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

01 Dec, 02:42


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን በአዋጅ ቁጥር 1112/2011 አንቀፅ 4/8  በተሰጠው ስልጣን መሠረት ብሔራዊ የመድኃኒት ፎርሙላሪ ያዘጋጃል፡፡ እንደ አስፈላጊነቱ ይከልሳል፡፡ በዚህም መሠረት የ3ኛዉ እትም ብሔራዊ የመድኃኒት ፎርሙላሪ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከመንግስትና ከግል ዘርፍ የተወጣጡ የሕክምና የመድኃኒትን ባለሙያዎች የቴክኒካል የስራ ቡድን ተቋቁሞ ለአንድ ዓመት ያህል ሲሰራ የቆየ ሲሆን  በጤና እና ፋርማሲዩቲካል ሳይንስ አዳዲስ ለውጦችን መሰረት በማድረግ እንዲሻሻል በማደርግ ተዘጋጅቷል፡፡
የተከለሰው ፎርሙላሪ በቅርቡ ስራ ላይ የዋለውን 7ኛውን እትም ብሔራዊ መሠረታዊ የመድኃኒት መዘርዝርን መሰረት አድርጎ የተዘጋጀ ሲሆን ፎርሙላሪው በተለያዩ ዙሮች ከተለያዩ ዩኒቨርስቲ እና ሆስፒታሎች በተወጣጡ የመስኩ ባለሙያዎች በምክክር እንዲዳብር ተደርጓል፡፡
ከህዳር 20-21/ 2017 ዓ.ም በአደማ  ከተማ በ3ኛው እትም ብሔራዊ የመድኃኒት ፎርሙላሪ ዙርያ የክልል ጤና ተቆጣጣሪ አካላት፣ የክልል ጤና ቢሮ የፋርማሲ አገልግሎት ባለሙያዎች እና ከተለያዩ ሆስፒታሎች የተወጣጡ ባለሙያዎች የተሳተፉበት የምክክር አውደ ጥናት ሲካሄድ የባለስልጣኑ የመድኃኒት ደህንነት ክትትልና የሕክምና ሙከራ መሪ ስራ አስፈፃሚ ተወካይ ኃላፊ አቶ ተሽታ ሹቴ እንደተናገሩት ብሔራዊ የመድኃኒት ፎርሙላሪ በየአምስት ዓመቱ መዘጋጀት ያለበት ሲሆን በዚሁ መሠረት የመጀመሪያው እና የሁለተኛው በ2000 እና በ2006 ዓ.ም ተዘጋጅቷል፡፡ ይሁንና 3ኛውም ብሔራዊ የመድኃኒት ፎርሙላሪ በ2011 ዓ.ም መዘጋጀት የነበረበት ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን መቆየቱን አስታውቀው በተለያዩ ባለድርሻ አካላት የዳበረው 3ኛው ብሔራዊ የመድኃኒት ፎርሙላሪው በቅርቡ በባለስልጣኑ ማኔጅመንት ፅድቆ ታትሞ ስራ ላይ  እንደሚውል አስታውቀዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

18 Nov, 06:03


#ዜና #EFDA /EFDA Weekly News /

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

14 Nov, 06:35


Ethiopian Food and Drug Authority Approves 7th Edition of Essential Medicines List.

The Ethiopian Food and Drug Authority (EFDA) has approved the 7th edition of the Essential Medicines List. This updated list, developed in collaboration with the Ministry of Health and other key stakeholders, incorporates recent technological advancements and addresses emerging diseases, helping Ethiopia’s healthcare system remain adaptive and resilient.

During a meeting held in Adama, EFDA Director General Heran Gerba emphasized the importance of regularly updating the Essential Medicines List, particularly for countries like Ethiopia. She highlighted that these updates are essential for minimizing drug wastage and enhancing access to vital medications across the nation.

The draft document was presented by Mr. Hailemariam Eshete from the Medicine Safety and Clinical Trial Lead Executive Office. Following a comprehensive discussion, the list was approved by a majority vote of EFDA’s management members.

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

14 Nov, 06:12


7ኛው መሰረታዊ የመድኃኒት መዘርዝር የመጨረሻውን ረቂቅ ሰነድ ፀደቀ


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ከጤና ሚኒስቴር እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን ወቅቱ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ ፣አዳዲስ የበሽታዎችን ስርጭት ታሳቢ በማድረግ ያዘጋጀው 7ኛው መሰረታዊ የመድኃኒት መዘርዝር በባለስልጣኑ ማኔጅመንት አባላት ፀደቀ፡፡

ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የተዘጋጀውን 7ኛው መሰረታዊ የመድኃኒት መዘርዝር ለማፅደቅ በአዳማ ከተማ በተዘጋጀው ውይይት ላይ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሔራን ገርባ እንደተናገሩት እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ሀገሮች መሰረታዊ የመድኃኒት መዘርዝር ማዘጋጀት እና መከለስ የመድኃኒት ብክነትን ከመቀነስም ሆነ የመድኃኒት አቅርቦቱን ከማሻሻል አኳያ ጠቀሜታው የላቀ መሆኑን ገልፀው የመድኃኒት መዘርዝሩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በሙሉ ተሳትፈውበት መዘጋጀቱን አስታውቀዋል፡፡

የመድኃኒት መዘርዝር ረቂቅ ሠነዱ ከመድኃኒት ደህንነትና የሕክምና ሙከራ መሪ ስራ አስፈፃሚ በተወከሉት በአቶ ኃይለማርያም እሸቴ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ከተካሄደበት በኋላ በማኔጅመንት አባላት በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

14 Nov, 05:51


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የአገልግሎት ሥነ-ምድብ (Service Taxonomy) ስልጠና ለአመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ሰጠ፡፡
ህዳር 02-03 ቀን 2017 ዓ.ም በአዳማ ከተማ በተዘጋጀው ሥልጠና ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ወ/ሮ አለምወርቅ እሸቴ የዋና ዳይሬክተር ጽ/ቤት ኃላፊ እንደተናገሩት የምንሰጠው አገልግሎት ህዝብና አገልግሎት ፈላጊውን ማህበረሰብ በብቃት በማገልገል ላይ የተመሰረተ የሰው ሀይል አስተዳደርን ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን ግልጽነትና ተጠያቂነትን እንዲሁም ብዝሀነትንና አካታችነትን ያረጋግጠ አስራር መዘርጋት ግባችን ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም ስልጠናውን በአግባቡ በመከታተል የአገልግሎት ስነ-ምድብ ሪፎርሙ መንግስትና ተገልጋይ ከኛ በሚጠብቀው ደረጃ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል በማለት ተናግሪዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

07 Nov, 08:59


https://t.me/ethiopianfoodanddrugauthority/5595

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

06 Nov, 14:46


https://t.me/ethiopianfoodanddrugauthority/5595

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

01 Nov, 08:33


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ከምግብ አምራች ተቋማት  ጋር በተዘጋጁ ረቂቅ መመሪያዎች ዙሪያ ምክክር አካሄደ፡፡


ከጥቅምት 21 እስከ 22/2017 ዓ.ም ተቋሙ  በምግብ  ማምረቻ  ተቋማት የቅድመ ፈቃድ  ቁጥጥር እና የምግብ  መልካም አመራረት ስርዓት ቁጥጥር አሰራር ረቂቅ መመሪያ ላይ ውይይት ተደርጓል።

በወይይቱ ላይ  የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባለስልጣኑ የምግብ ኢንስፔክሽን ህግ ማስፈፀም መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ ሙላት ተስፋዬ እንደተናገሩት በረቂቅ መመሪያው ላይ ውይይት ያስፈለገው  የምግብ አምራች  ተቋማት በዘርፉ ካለቸው ክህሎት፣  ዕውቀትና ልምድ ተነስተው  በምግብ ቁጥጥር መመሪያው ጥሩ ግብዓት ማበርከት ስለሚችሉ፣ አከታችነትን  ለማስፈን እና  የተሳለጠ  የቁጥጥር ስራን በጋራ ለመስራት ስለሚያስችል ነው ብለዋል፡፡

የምግብ ማምረቻ ተቋማት የቅድመ ፈቃድ ቁጥጥር  ረቂቅ መመሪያውን  ያቀረቡት የተቋሙ የምግብ ምዝገባና ፍቃድ መሪ ሥራ አስፈጻሚ  አቶ  መንግስቱ አስፋው በበኩላቸው የቁጥጥር መመሪያዎችን  በየጊዜው ማሻሻልና ከወቅቱ  ጋር ማጣጣም እንዲሁም  በቴክኖሎጂ መደገፍ እና ከባለድርሻ ጋር ማዳበር የተሻለና ሊያሰራ የሚችል መመሪያ ለማዘጋጀት ያግዛል  ብለዋል፡፡

በውይይቱ ላይ ከ70 በላይ የምግብ  አምራች  ተቋማት  ባለቤቶች ፣ ስራ አስፋጻሚዎች እና ተወካዮች የተገኙ ሲሆን በተካሄደውም ውይይት የተነሱ ሃሳቦችና አስተያየቶች በግብዓትነት ተወስደው  በመመሪያው ውስጥ የሚከተት መሆኑ ታውቋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

30 Oct, 11:49


#ስለ #አስገዳጅ #የበለፀገ #ምግብ #ደረጃዎች

ሀገራት በህብረተሰብ ላይ የሚታዩ ከፍተኛ የንጥረ ነገር እጥረትን ለመቅረፍ በስፋት ጥቅም ላይ የሚዉሉ ዋነኛ ምግቦችን ማበልፀግ ዋነኛ ስትራቴጂ ሆኖ ያገለግላል፡፡

በሀገራችንም በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ እጥረት እንዳለ በተለዩ ንጥረ ምግቦችን በመለየት የምግብ ጨዉ በአዮዲን፣የምግብ ዘይትን በቫይታን ኤ እና ዲ3 እንዲሁም የስንዴ ዱቄትን በቫይታሚን ቢ እና ዚንክ አምራቾች አበልጽገዉ ምርታቸዉ ላይ ብሔራዊ የበለፀገ ምግብ ሎጎ ለጥፈዉ ለህብረተሰቡ እንዲያቀርቡ አስገዳጅ ደረጃ ወጥቶ ተግባረዊ እየተደረገ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ህብረተሰቡ እነዚህን በአስገዳጅነት እንዲበለፅጉ ደረጃ የወጣለቸዉን ምግቦች ሲገዛ የበለፀጉና የበለፀገ ምግብ ምልክት የለጠፉትን ብቻ በመጠቀም በንጥረ ምግብ እጥረት ሊመጣ የሚችልን የጤና ችግር ራሱንና ቤተሰቡን እንዲጠብቅ እንጠይቃለን፡፡

አምራች ድርጅቶችም በደረጃዉን መሰረት የሚያመርቱትን ምግብ አበልፅገዉና የበለፀገ ምግብ ምልክቱን ለጥፈዉ ለህብረተሰቡ እንዲያቀርቡ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

30 Oct, 09:10


#አስገዳጅ #ምግብ #ደረጃ #የወጣላችው #ምርቶችን #ሲጠቀሙ እነዚህን #መሰረታዊ #ጉዳዮች #ያስተውሉ፡፡

ምግብ ደረጃዎች አንድ ምግብ በዋናነት በፊዚካል፣ኬሚካል፣ማይክሮባዮሎጂካል፣የአስተሻሸግ፣የገላጭ ፅሁፍ ሊያሟላቸዉ የሚገባ መስፈርቶች በመደንገግ ጥራቱና ደህነቱን ለማረጋገጥ ይጠቅማሉ፡፡የተወሰኑ የምግብ ደረጃዎች አስገዳጅ ሆነዉ እንዲፀድቁ የተደረጉ ሲሆን በዚህም በየጊዜዉ ምርመራ በማድረግ መስፈርቱን ማሟላታቸዉን በማረጋገጥ ብሔራዊ አስገዳጅ ደረጃ ሰርተፊኬት ፈቃድ አግኝተዉ ምርትቸዉን ላይ ብሔራዊ ደረጃ ምልክቱን ለጥፈዉ መዉጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡
እነዚህ ብሔራዊ አስገዳጅ ደረጃ ወጣላቸዉና የደረጃ ምልክቱን ምርታቸዉ ላይ ለጥፈዉ መዉጣት የሚጠበቅባቸዉ በሀገር ዉስጥ የተቀነባበሩ ምግብ ምርቶች እንደ
• ፓስቸራይዝድ ወተት፣
• የለዉዝ ቅቤ፣
• የምግብ ጨዉ፣
• ለስላሳ መጠጥ፣
• ቢራ፣
• የታሸገ ዉሃ፣
• የታሸገ ህፃናት ምግብ እና
• ሱፐር የጥራጥሬ እና አኩሪ አተር ቅልቅል(SC-CSBP)

ህብረተሰባችን ከላይ የተዘረዘሩን የምግብ ምርቶች የወጣዉን ደረጃ የተገበሩና የደረጃ ምልክቱን የለጠፉትን ምርቶችን ብቻ በመጠቀም ጥራትና ደህንነታቸዉን የጠበቁ ምርቶችን እንዲጠቀም እንጠይቃለን፡፡
የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

29 Oct, 14:49


ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የ100 ቀን ዕቅድ አፈጻጸም እና የባለስልጣን መ/ቤቱ የሩብ ዓመት አፈጻጸም ላይ ውይይት ተደረገ፡፡
ጥቅምት 19/2017 ለምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ሠራተኞች በማክሮ ኢኮኖሚ ፋይናንስ ሪፎርም ላይ ገለፃ ያደረጉት የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ወሪ/ት ሄራን ገርባ እንደተናገሩት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙ በዋናናት ሲደረግ ትኩረት የተደረገው በሁሉም ዘርፍ አቅርቦትና ፍላጎትን ማጣጠም ፣ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን በዘላቂነት ማሳደግ ፣ ምርትና ምርታማነትን መጨመር፣ የዜጎችን አካታች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን መፍጠር ፣የውጭ ኢንቨስትመንትን መሳብና ሁለንተናዊ አገራዊ ዕድገት ማምጣት ነው፡፡
ኃላፊዋ አክለውም በዚህም በጎ ለውጦች የታዩ ሲሆን የውጭ ምንዛሬ በስፋት መገኘት፣ የውጭ ኢንቨስትመንት መጨመር፣ የወጪ ንግድ ማደግ፣ የኮንትሮባንድ ንግድ መቀነስ እና ገቢ የመሰብሰብ መጠናችነን ማደግ መገለጫዎቹ ናቸው ብለዋል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ ልንሻገራቸው የሚገቡን ተግዳሮቶች መኖራቸውን የጠቀሱት ወሪ/ት ሄራን ገርባ የዋጋ ግሽበት እና የስራ ዕድል ፈጠራ አበክረን ልንሰራበት የሚገባን ዘርፍ ነው ብለዋል፡፡ በመሆኑም የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሙን ስንገመግም ከተቋሙ ጋር ተዛማጅነት ያላቸዉን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርሞች ወስደን ልንሰራባቸዉና የራሳችንን አበርክቶ ማስቀመጥ አለብን ሲሉ አሳስበዋል፡፡
በመጨረሻም የ2ዐ17 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የምግብና የጤና ግብዓት ቁጥጥር ዕቅድ አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው በቀጣይ ሩብ ዓመት ትኩረት ሰጥቶ ሰራተኛው በመቀናጀት በላቀ ሁኔታ ህብረተሰብን ለማገልገል መስራት እንደሚያስፈልግ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

29 Oct, 06:27


https://youtu.be/pyPn6fWmg-I?si=Gdn1KM1ktkPK8M7u

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

26 Oct, 17:02


የ2ዐ17 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የምግብና የጤና ግብዓት ቁጥጥር የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ፡፡

ጥቅምት 16/2ዐ17 ዓ.ም በተካሄደው ግምገማ የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር ወሪ/ት ሄራን ገርባ አንደገለጹት የዝግጅት ምዕራፍን ከወትሮ ለየት ባለ መልኩ ቀደም ብሎ በማጠናቀቅ ወደ ተግባር የተገባበት ጊዜ መሆኑን ጠቅሰው የተቀመጡ ኢላማዎች መሳካታቸው የሚታይበት መድረክ በመሆኑ የህብረተሰብን ጤና ከመጠበቅ አንጻር ከምግብና የጤና ግብዓቶች ደህንነትና ጥራት ለማረጋገጥ የተሰሩ ስራዎች ጠንካራ ስራዎችና ያጋጠሙ ችግሮች መፍትሄ አቅጣጫ የሚቀመጥበት መድረክ ነው ብለዋል፡፡

በተጨማሪም ባሳለፍነው የሩብ ዓመት የአገልግሎትና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም እንዲሁም የማቹሪቲ ደረጃ ሶስት ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸው ጠቅሰው የቁጥጥር ዘርፉን ለማዘመን፤ከአፍሪካና ከአለም አቀፍ አንፃር ተፎካካሪ ሆኖ ለመውጣት የመንሰራበት ወቅት መሆኑን አሳውቀዋል፡፡

የማክሮ ፋይናንስ ሪፎርም ከተደረገ በኋላ ብዙ በጎ ለውጦች የታዩ በመሆኑ ከለውጦቹ ጋር ተያይዞ የፎሬይን ከረንሲ እድል በስፋት መገኘቱና የውጭ ኢንቨስትመንት መጨመር ጋር ተያይዞ አዲስ ጥያቄዎች እና እድሎች መኖራቸውን ገልፀው የምግብና የጤና ግብዓት ቁጥጥሩን ተግባር ከዚህ ጋር ማዛመድና ማጠናከር እንደሚገባ በማስገንዘብ በእጅ ያለ ሀብትን በአግባቡ በመለየት በቁጠባ በመጠቀም ስራዎችን እያላቁና እያዘለቁ ውጤታማነትን ለማረጋገጥ መስራት አስፈላጊ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የዕቅድ አፈፃፀም ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ጠንካራና ደካማ ጎኖች ተለይተው በቀጣይ ሩብ ዓመት ትኩረት ተሰጥቶ የምግብና የጤና ግብዓት ቁጥጥር ስራ በቅንጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በላቀ ሁኔታ ህብረተሰብን ለማገልገል መስራት እንደሚያስፈልግ አቅጣጫ ተሰጥቷል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

26 Oct, 11:29


https://youtu.be/BOJnKTv2p98

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

26 Oct, 11:26


https://youtu.be/10HEBzs2qZ0

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

25 Oct, 15:09


ባለስልጣን መ/ቤቱ እና ክልል ተቆጣጣሪ አካላት ጋር የመድኃኒት ዘርፍ ቁጥጥር የዓለም አቀፍ የማቹሪቲ ደረጃ -3 ለማሳካት እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ትግበራ ያለበትን ደረጃ ገመገመ፡፡

ጥቅምት 15/2ዐ17 ዓ.ም ማቹሪቲ ደረጃ-3/ሶስት/ ከክልል ጤና ተቆጣጣሪ ኃላፊዎችና ከቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች ጋር በተደረገው የግምገማ መድረክ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ወሪ/ት ሄራን ገርባ እንደ ገለጹት በሀገር ደረጃ ማቹሪቲ ደረጃ-3 /ሶስት/ ለማግኘት በጠየቅነው መሠረት የአለም ጤና ድርጅት በሰኔ 23/2ዐ24 የኦዲት ካደረገ በኋላ ስምንት ማስተካከያዎች /Recommendation/ ሰጥተዋል፡፡ይህንን መሰረት በማድረግ ሁሉን አቀፍ የኦዲት አሰራር ስርዓት በመሆኑ በባለስልጣኑ፣ በባለድርሻ አካላት እና በክልል ተቆጣጣሪ አካላት መሰራት ያለባቸውን ስራዎች በመለየት በቅንጅት በዕቅድ ሲሰሩ እንደነበሩና የአለም ጤና ድርጅትም በቨርችዋል ስራዎቻችንን በየደረጃው እየገመገሙ መጥተዋል፡፡በመሆኑም ከአንድ ወር በኋላ በአካል ሲመጡ በሰጡት ማስተካከያዎች ላይ አካላዊ የኦዲት የሚያደርጉ በመሆኑ ቀሪ ስራዎችን ከወዲሁ ተቀናጅተን በመስራት ማጠናቀቅ ይገባናል ብለዋል፡፡
በክልል ጤና ተቆጣጣሪ ቢሮዎች እየተሰሩ ያሉ የጥራት ስራ አመራር ተግባራት ጥሩእንደሆኑ ጠቅሰው ቀሪ ስራዎችን በቁጭት ማከናወንም እንደሚገባ አሳውቀዋል፡፡የመድኃኒት ቁጥጥር ዘርፍ የዓለም ዓቀፍ የማቹሪቲ ደረጃ ሶስት ሟሟላት የክትባት መድኃኒቶች በአገር ውስጥ ከማምረት ጀምሮ የተለያዩ እድሎች እንደ ሀገር የሚፈጥር መሆኑንም አስገንዝበዋል፡፡በተጨማሪም የዓለም ዓቀፍ ደረጃ የመድኃኒት ቁጥጥር ስርዓት ደረጃን ማሳካት ከምንም በላይ ህዝባችን ደህንነቱ ፣ጥራቱና ፈዋሽነቱ የተረጋገጠ መድኃኒት በወጥነት እንዲደርሰው ለማድረግ ያደርጋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

25 Oct, 09:36


https://youtu.be/xzlZEVUpPu8

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

25 Oct, 07:45


https://youtu.be/B6Km3Eg0v7c?si=oAwJRFIC8fNSN4ok

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

25 Oct, 06:58


#ሁላችንም ቶሎ #እንዲሻለን እንፈልጋለን፤
#በሀኪም #የታዘዘልንን መድኃኒትን #በአግባቡ በመጠቀም፣ ጤናማ ሆነን እንኑሩ!

ሁላችንም በፍጥነት እንዲሻለን እንፈልጋለን። ነገር ግን መድኃኒትን በተመለከተ ትንሽ እውቀት ረጅም መንገድ ያስኬዳል እንደሚባለው በሀኪም የታዘዘልንን መድኃኒት በአግባቡ መጠቀም የህክምና ባለሙያ መመሪያ እና ትዛዝ መከተል ብቻ ሳይሆን ጤናዎን የመጠበቅና አግባባዊ ካልሆነ የመድኃኒት አጠቃቀም ችግር በጤና ላይ ከሚያስከትለው አደጋ እራስን እና ህብረተሰብን ለመጠበቅ መረጃ ላይ የተመሰረተ ምርጫ ማድረግ ነው።

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

23 Oct, 18:40


አግባብ ያልሆነ የፀረ ወባ መድኃኒቶች አጠቃቀም ለእርስዎ፣ ለልጅዎ፣ እንዲሁም ለህብረተሰቡ ጎጂ መሆኑን በመገንዘብ የፀረ ወባ መድኃኒቶችን በጤና ባለሙያ ትዕዛዝ ብቻ በመውሰድ መድኃኒቱን የሚቋቋሙ የወባ ጥገኛ ዝርያዎች እንዳይፈጠሩ ይከላከሉ፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

23 Oct, 06:39


በኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት 702,050.00 ሺ ብር በላይ የሚገመቱ ህገ-ወጥ የወባ መድኃኒቶች እና ከ2,197,015 ሚሊዮን በላይ ህጋ-ወጥ የምግብ ምርቶችን መያዙን አስታወቀ፡፡

ጥቅምት 11/2017 ዓ.ም የቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጁሀር አበጋዝ እንደገለፁት ከክልል ተቆጣጣሪ አካላት ጋር በመሆን በወባ መድኃኒቶችና ሌሎች ህገ-ወጥ መድኃኒቶች ላይ በደሴ ኮምቦልቻና ሀረቡ ላይ በ86 ተቋማት ላይ የቁጥጥር ስራ ተሰርቷል፡፡ ግምቱም 702,050.00 ሺብር   የሆነ ህገ-ወጥ የወባና ሌሎች መድኃኒቶች እንዲሰበሰቡ ተደርገዋል፡፡
በሌላ በኩል በህብረተሰቡ ጥቆማ ደሴ ላይ ባለ አንድ ሊትር ዘይት የታዋቂ ብራንድ ስም በመጠቀምና በሀሰተኛ አስተሻሸግ፤ የአገልግሎት ጊዜና ማብቂያ የሌለው 92 ደርዘን ዘይት ከንግድ መምሪያና ከደሴ ከተማ ጤና ተቆጣጣሪዎች ጋር በመሆን እንዲሰበሰብ ተደርጎል፡፡በተጨማሪም ከህብረተሰቡ በተሰጠው ጥቆማ የጨቅላ ህጻናት ምግብ፣ምንጩ የማይታወቅና የተበላሸ የዱቄት ወተት፣የተለያዩ ከረሜላዎችና ዘይቶች እንዲሰበሰቡና እንዲወገዱ ተደርጔል፡፡
የቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ እንደገለጹት 1,680 ኩንታል የሆነ ኮንትርባንድ ጥሬ ጨው ግምታዊ ዋጋው 1,600,000 ብር የሆነ ህገ-ወጥ የጨው ምርት ወደ መጣበት ቦታ በፌደራል ፖሊስ ታጅቦ እንዲመለስና ጥቅም ላይ እንዳይውል ተደርጔል፡፡
  ኃላፊው አክለውም በሰመራና ኮምቦልቻ መግቢያና መውጫ ኬላ በተሰራ የኮንሳይመንት ምርመራ ከሚጠየቅባቸው ሰባት የምግብ ዓይነቶች ውስጥ 41 ጊዜ የኮንሳይመንት ምርመራ ተሰርቶላቸው ሁሉም አልፈዋል ብለዋል፡፡

በወጪ እና ገቢ ምግብ ላይ አስፈላጊዉን የደህንነትና የጥራት ቁጥጥር በማድረግ 960.00 ቶን ወጪ እና 175‚242 ሺ ቶን ምግብ መልቀቂያ ፍቃድ የተሰጣቸው መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

22 Oct, 13:08


በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የደቡብ ምሥራቅ አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በያዝነው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሦስት ወራት ከ238 ሺ ቶን በላይ ምግብ እና ከ86 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው መድኃኒቶች ላይ ተገቢውን ቁጥጥር በማድረግ ወደ አገር ውስጥ ገብተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ ፍቃድ መስጠቱን አስታወቀ፡፡

የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ ገዛኸኝ እንዳለ እንደተናገሩት ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከ238 ሺ ቶን በላይ ምግብ እና ከ86 ቢሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው መድኃኒቶች የመልቀቂያ ፍቃድ በመስጠት ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ ያደረገው አስፈላጊውን የጥራትና የደህንነት ፍተሻ በላቦራቶሪ ጭምር አድርጎ በማረጋገጥ ነው፡፡

ኃላፊው አክለውም በተመሳሳይ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በያዝነው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሦስት ወራት ከ15 ሺ ቶን በላይ የምግብ ጥሬ ዕቃ እና ከ363 ሚሊዮን ብር ዋጋ ያላቸው የመድኃኒት ጥሬ ዕቃዎች ላይ አስፈላጊውን ቁጥጥር በማድረግ ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ የመልቀቂያ ፍቃድ ሰጥቷል፡፡

በሌላ በኩል ከ8.8 ቢሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የሕክምና መሣሪያዎችና መገልገያዎች በተጠቀሰው ወራት አስፈላጊውን የጥራት መስፈርት ማሟላታቸው በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ተረጋግጦ ወደ አገር ውስጥ እንዲገቡ የመልቀቂያ ፍቃድ መስጠቱን አቶ ገዛኸኝ ጠቁመዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ አስፈላጊውን መስፈርት ላሟሉ 40 የምግብ ተቋማት የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት የሰጠ ሲሆን ኦዲቲንግ መሰረት ያደረገ የድህረ ፈቃድ ኢንስፔክሽን በተለያዩ የምግብ አስመጭ እና አከፋፋይ ድርጅቶች ላይ መከናወኑንና ቁጥራቸው 35 በሚሆኑ በእነዚሁ ተቋማትም የውስጥ የጥራት ስርዓት እንዲዘረጉ መደረጉን ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ኃላፊ ከአቶ ገዛኸኝ እንዳለ ገለፃ ለማወቅ ተችሏል፡፡

EFDA የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን

21 Oct, 11:43


የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን የህፃናት ማቆያ አዘጋጅቶ አስመረቀ፡፡

ጥቅምት 11/2017 አዲስ አበባ፡ የባለስልጣኑ አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ያስገነባውን የህፃናት ማቆያ መርቀው የከፈቱት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ወ/ት ሔራን ገርባ እንደተናገሩት ከዚህ ቀደም የተወሠኑ ሰራተኞች በህፃናት ማቆያ እጥረት ከስራ ገበታቸው ፈቃድ ውስደው ይቀሩ እንደነበርና ከአቅም በላይ የሆነባቸውም ስራ መልቀቃቸውን አስታውሰው በዛሬው እለት በደቡብ ምስራቅ አዲስ አበባ በሚገኘው ቅርንጫፍ የተመረቀው የህፃናት ማቆያ የሠራተኞችን ችግር እንዲፈታ የጤና ባለሙያዎችና ተንከባካቢዎች እንደዲኖሩት መደረጉን ገልፀዋል፡፡
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ቃሊቲ አካባቢ ከመንግስት በወሰደው መሬት የልህቀት ማዕከል እየገነባ መሆኑን የጠቆሙት ዋና ዳይሬክሯ በማዕከሉም ከተለያዩ የስራ ክፍሎችና የስልጠና ማዕከል በተጨማሪ የህፃናት ማቆያ እንደሚኖር ገልፀው ግንባታው ሲጠናቀቅ ችግሩን በዘላቂነት የሚፈታ መሆኑን ጨምረው ተናግረዋል፡፡
የብቃትና ሠው ሀብት ስራ አስፈፃሚ አቶ ሠለሞን አምዴ በበኩላቸው በምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ እንደተናገሩት የፌዴራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ 1064 ሁሉም የፌዴራል መስሪያ ቤቶች የህፃናት ማቆያ እንዲኖራቸው እንደሚያስገድድ ገልፀው በአሁኑ ወቅት 36 ሴት ሰራተኞችና 11 ወንድ ሰራተኞች ከ3 ዓመት በታች ህፃናት ያሏቸው ሲሆን የዚህ ማቆያ መገንባት ለሠራተኞች ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ነው

7,435

subscribers

4,490

photos

76

videos