ቀና ብዬ ሳያት አይኔ ማረፊያ አጣ ከላይ እስከታች አያት ጀመር አይኗ ሰማያዊ ሆኖ እጅግ የሚስብ እና የሚያየውን ሁሉ የሚማርክ ነው ይህን አይን ማየት ከሲኖ ትራክ ጋር መጋጨት ሆኖ ተሰማኝ እንደምንም ተጋፍጬ እእእ ይቅርታ••• በእኔ ምክንያት ጓደኞቼ ስለ ተናገሩሽ
" ይቅርታ እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ አለችኝ በትህትና ? "
ባልፈልግ እጠይቅሽ ነበር አልኩኝ ግራ በመጋባት
" እሺ ጥሩ ከዚህ በኋላ ሴት እንዳትላከፍ አለችኝ "
ውይይ ይሄን እንኳን በቶሎ ማቆም የምችል አይመስለኝም ምክንያቱም ጓደኞቼ እንደ ሞኝ ነው የሚቆጥሩኝ አልኳት
" ስለዚህ ይቅርታህም ከልብ አይደለም ማለት ነው አለችኝ "
እንዴ ምን አገናኛቸው እኔ ግን ከልቤ ነው ይቅርታ የጠየቅኩሽ አልኳት
" ከልብህ ወስነህ ይቅርታ መጠየቅ ከቻልክ ከልብህ ወስነህም መላከፍ ማቆም አይከብድህም ደግሞ የሚላከፍ ሰው ግራ የሚላከፍ ደግሞ አራዳ ነው ብለህ ማሰብ የለብህም አለችኝ "
እሺ ቢከብደኝም አንድ ሳምንት ስጪኝ አደርገዋለው ••••
" ካመንክበት ዛሬ ማቆም ትችላለህ ••• "
አይ ግድ የለም አንድ ሳምንት ስጪኝ •••• እና ደግሞ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ እፈልጋለው
" ምንድን ነዉ አለችኝ "
ግን በእናትሽ እንዳትቀየሚኝ መልሱን ማወቅ ለእኔ በጣም ስለሚያስፈልገኝ ነው
" እሺ አልቀየምህም "
ፍቅረኛ ኖሮሽ ያውቃል አሁንስ ፍቅረኛ አለሽ••••
" በጣም ከባድ ጥያቄ ነው አለች ፈገግ ብላ "
ፈገግታዋን አይቼም ልቤ ጨዋ ናት ጨዋ ናት እያለ ብቻውን በሰውነቴ ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ ታወቀኝ••••• እና እእእ መልሱ ምንድን ነው አልኳት
" በቃ እኔም መልሱን የዛሬ ሳምንት እነግርሃለው አንተም ግን መላከፍ ማቆም አለብህ አለችኝ "
እሺ ቢረዝምብኝም እጠብቃለው ግን እኮ ስምሽን አልነገርሽኝም አልኳት
" ወንጌል እባላለው ብላ እጇን ዘረጋች "
ሀይሌ እባላለው አልኩኝ እና እጄን ዘርግቼ ጨበጥኳት
" በቃ በል ሰላም ሁን ብላኝ ሄደች "
እኔም እየተንተባተብኩ ወንጌል ብዬ ጠራኋት
" አቤት ብላኝ ዞር ስትል "
ስልክ እኮ አልሰጠሽኝም ሳምንት በምንድን ነው የማገኝሽ አልኳት እየፈራው
" እመጣለው በዛሬው ሰአት ብቻ ያዘዝኩህን አትርሳ ብላኝ ሄደች "
ክፍል አራት 30 like ሲሞላ ይቀጥላል ይቀጥላል
ለማንኛውም አስተያየት
https://t.me/+oAOHKAMJmd1kYTE0