ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር @degnitkindness Channel on Telegram

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

@degnitkindness


"ወደ ደግነት በጎ አድራጎ ማህበር እንኳን በደህና መጡ" የድግነት ዋናው አላማ ለተቸገሩ ያቅማችንን ማድረግ እና እርስ በርሳችን መጠያየቅ መረዳዳት ነው

✍️ "ደግነት የአቅም ጉዳይ ሳይሆን የልብ ጉዳይ ነው "
ባለን ነገር ሁሉ እንረዳዳ፤እንተዛዘን
👉"ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው"👈
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
( 1000532242685 )
ናትናኤል ታደለ እና ቴዎድሮስ አበራ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር (Amharic)

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር በደግነት ምንጭ ያሉ ሰዎችን ለእነዚህ የምግብ ጋዜጣዊ መረጃዎች እና እናቴማችንን ያቅርብ እንዲለም ነው ፡፡ "ደግነት የአቅም ጉዳይ ሳይሆን የልብ ጉዳይ ነው"፣ ባለን ነገር ሁሉ እንረዳዳ፣ እንተዛዘን "ሰው ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው" ፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ (1000532242685) ናትናኤል ታደለ እና ቴዎድሮስ አበራ ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Feb, 13:34


🛑 ስለ ሀይማኖቴ ማወቅ ግዴታዬ ነው የሚል የማንኛውም ኦርቶዶክስ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል።  ጥያቄ ይጠየቃል ምዕመኑም ይሳተፋል ቻናሉን ለመቀላቀል

     🔐ከስር ክፈት የሚለውን
     በመጫን ይቀላቀሉ👇👇👇

ክፈት      ክፈት          ክፈት               
ክፈት       ክፈት        ክፈት
ክፈት       ክፈት        ክፈት       

................♥️♥️♥️..................

ክፈት        ክፈት           ክፈት        ክፈት        ክፈት           ክፈት     
ክፈት        ክፈት           ክፈት

.................💠💠💠..................
                                                 
ክፈት           ክፈት          ክፈት ክፈት          ክፈት          ክፈት   
ክፈት           ክፈት           ክፈት

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Feb, 11:36


👉Open የሚለውን ንኩ የፈለጋችሁትን 🎧 የአቢይ ጾም መዝሙሮችን ታገኛላቹ።


1.ኑ እንቅረብ................Open

2.ለንሰሐ ሞት አብቃኝ ..........Open

3.ዘጾም ወጸለየ ...............Open

4.ይሁዳ የሸጠው ...........Open

5.ሃቅዱስ ቅዱስ ............Open

7.ሰላም ለኪ ..............Open

.
.

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Feb, 09:57


🔴 ኦርቶዶክስ ኖት ❓️



           🌹🌹🌹
         🌹🌹🌹🌹 
      🌹🌹🌹🌹🌹
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹
      🌹🌹🌹🌹🌹
         🌿🌹🌹🌿
              🌿🌿
                 🌿                         
                  🌿               🌿🌿
                 🌿           🌿🌿🌿
                🌿      🌿🌿🌿🌿
               🌿    🌿🌿🌿🌿
              🌿 🌿🌿🌿🌿
               🌿 🌿🌿🌿
                 🌿
                  🌿
                   🌿
                    🌿
                    🌿
                  🌿
     
         🔴የአበባውን ምስል አንድ ጊዜ በመጫን ጠቃሚ ነገር ይመልከቱ አንድ ጊዜ ብቻ ይንኩት፡፡

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 20:03


እሽ ለተሳተፋችሁ በሙሉ እግዚአብሔር አምላክ ቃለ ህይወትን ያሰማልኝ በእድሜ በፀጋ ይጠብቅልኝ ያገልግሎት ዘመናችሁን ይባርክልኝ በቤቱ ያፅናችሁ ወገኖቼ አንድ ነገር ልንገራችሁ ለሁሉም ሰው የምመኘው ለቀኑ ያብቃችሁ ያዘጋጃችሁ እባካችሁ ማንም ያንን የሚያስፈራ እሳት አይይ ወገኖቻችንን በፀሎት እናስባቸው ከቤተ ክርስቲያን ስርዓት ውጭ ላሉት ይመለሱ ዘንድ እንፀልይ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችንን እናስብ ሀገራችንን ህዝባችንን እንጎብኝ እርስ በእርስ እንዋደድ ማህበራችንን ማህበረ ደግነትን እንዲጠብቅልን ምዕመኑን እንዲያስብልን እንፀልይ እመቤታችን ፀሎታችን ከደመና በታች እንዳይቀር እንድታሳርግልን ከአንድ ልጇ እንድታማልደን እንፀልይ ያዘኑትን እንዲያፅናናልን እንፀልይ የተራቡትን እንዲመግብልን እንፀልይ የታረዙትን እንዲያለብስልን እንፀልይ የተጠሙትን እንዲያጠጣልን እንፀልይ የተሰደዱትንም እንዲያስብልን እንፀልይ ወገኖቼ እንፀልይ እኔንም በአለም የደከምሁ ነኝ እና በፀሎታችሁ እስቡኝ
አስጀምረው ላስፈፀሙን ለእናትና ልጁ ክብር ይሁን🙏
የሳምንት ሰው ይበለን በነገው እለትም መርሀ ግብር ይኖራል እንዳንቀር አደራ



መልስ
1, መ ሮሜ 14:1
2, ሐ ሮሜ 13:12
3, መ
4, ሐ ሮሜ 1:7
5, ሠ
6, በአገዛዝ : በስልጣን: በመለኮት
7, ?

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:48


ሁሉ በእጅጉ ሲገረምና ‹‹በአምላከ ታዴዎስ ስም አምናለሁ›› ሲል የባለጸጋው ልጅ ሙሳ ግን ‹‹በምትሃት አሳይቶን ነው እንጂ የእውነት አይደለም›› በማለት አባቱንም እንዳያምን ይናገር ጀመር፡፡ ይህንንም ሲናገር በመጀመሪያ ያለፈችው እናቲቱ ግመል እረግጣ ገደለችው፡፡

አቡነ ታዴዎስም ንጉሡን፣ አባቱን አፍጃልንና ሕዝቡን የሞተ እንደሚነሣ ሲያስምሯቸው ‹‹የሞተ ይነሣልን? እስኪ ይህ የሞተው ልጅ ይነሳና ሁሉም አይቶ ይመን›› አሏቸው፡፡ እሳቸውም ‹‹ዛሬ ተቀብሮ ይዋልና ነገ በሦስተኛው ይነሣል›› ብለዋቸው ተቀብሮ ዋለ፡፡ በማግሥቱም አፍጃልን ጠርተው ‹‹‹አልዓዛርን ከሞት ባስነሣው በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ልጄ ሆይ ና ውጣ› ብለህ ከልጅህ መቃብር ላይ አኑረው› ብለው ዘንጋቸውን ሰጡት፡፡ ሄዶም እንዳሉት ቢያደርግ ልጁ አፈፍ ብሎ ተነሥቷል፡፡ ይህንን ያዩ የሀገሩ ሰዎች ሁሉም አምነው ተጠምቀዋል፡፡ እሳቸውም 12 አብያተ ክርስቲያናትን አሳንጸው ሞቶ የተነሳውን ሙሳን ሙሴ ብለው ሰይመው አስተምረው ሊቀ ካህናት አድርገው ሾመውት አቡነ አኖሬዮስን ይዘው ወደ ጽላልሽ ዞረሬ ተመልሰዋል፡፡

አቡነ ተክለ ሃይማኖት ካረፉ በኋላ አባ ያዕቆብ የተባሉ ጳጳስ ከግብፅ መጡ፡፡ የአቡነ ታዴዎስን ዜና ሲሰሙ ተደስተው ከአቡነ ፊሊጶስ ጋር ሆነው አስጠርተዋቸው ‹‹የአባታችሁን ዜና ገድል ንገሩኝ›› አላቸው፡፡ አቡነ ታዴዎስም ‹‹ጨዋታ በአስተርጓሚ አይሰምርም›› ብለው ወደ ጌታችን ቢጸልዩ የጳጳሱ ቋንቋ ለታዴዎስ፣ የታዴዎስም ቋንቋ ለጳጳሱ ተገልጦላቸው የመሸ የነጋ ሳይመስላቸው 40 ጾምን ሲጨዋወቱ ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በኋላ ጳጳሱ ከንጉሡ ተማክረው ‹‹ሊቀ ካህናት ዘጽላልሽ›› ብለው ሾመዋቸዋል፡፡

በነግህና በሰርክ ቤተ ክርስቲያንን እያገለገሉ፣ ቀን ወንጌልን እየሰበኩ፣ ሌሊት ከባሕር ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በታላቅ ተጋድሎ እየኖሩ ሳለ ከ10 ዓመት በኋላ ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ቅምጥ አገባ፡፡ አቡነ ታዴዎስም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ ገሥጸውና አውግዘው አቡነ ማትያስን አስከትለው ሲመለሱ ቅምጧ የንጉሡ ሚስት በፈረስ ተከትላ ደርሳ የኋሊት አሳስራ ዛሬ ‹‹ማርያም ገዳም›› ከሚባለው ቦታ ፊት ለፊት ካለው ትልቅ ገደል ውስጥ ሁለቱንም ጣለቻቸውና ጥር 29 ቀን በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡

በሰማዕትነት ዐርፈው ደማቸው ከፈሰሰበት ከገደሉ ስር በፈለቀው ጸበላቸው ‹‹ታዴዎስ ወማትያስ›› እያለ ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ እያለ የተጠመቀ ሰው እንደ 40 ቀን ሕፃን እንደሚሆን ጌታችን ቃልኪዳን ገብቶላቷቸዋል፡፡ ይህ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ የተሠራው ቤተ ክርስቲያናቸው በጠላት ወረራ ጊዜ ፈርሶ ቦታው ጠፍ ሆኖ የኖረ ቢሆንም የአካባቢው ሕዝብ ቦታውን ከልሎ በክብር ሲጠብቀው ስለኖረ ፈቃደ እግዚአብሔር ሆኖ የአቡነ ታዴዎስ ታቦታቸው በ2005 ዓ.ም ከኢቲሣ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ወጥቶ ጻድቁ ሰማዕትነት በተቀበሉበት አካባቢ በተሠራው መቃኞ ቤተ ክርስቲያናቸው በታላቅ ክብር ገብቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያኑም ከኢቲሣ በእግር የአንድ ሰዓት ተኩል ርቀት ላይ ይገኛል፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ጻድቃን_ቅዱሳን_ማሕበረ_ዶጌ (ዴጌ ጻድቃን)

በዚህች እለት የጻድቃን ቅዱሳን ማኅበረ ዶጌ አክሱም አካባቢ በቁጥር ወደ 3000 የሚሆኑ ከመድኃኔዓለም ጋር ማኅበር ይጠጡ የነበሩ በአንድ ላይ የተሰወሩ ቅዱሳን መታሰቢቸው ነው፡፡ እነዚህም ጌታችን መድኃኔዓለም ክርስቶስ በመካከላቸው ተገኝቶ የጽዋ ማኅበራቸውን አብሯቸው የጠጣ ሦስት ሺህ ቅዱሳን ‹‹ማኅበረ ጻድቃን ወይም ማኅበረ ደጌ›› እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ ማኅበሩን ያቋቋመው ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ነው፡፡ በኋላም ከመድኃኔዓለም ክርስቶስ ጋር አብረው ማኅበር የጠጡ እነዚህ ሦስት ሺህ ቅዱሳን አክሱም አካባቢ ባለው በአቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ገዳም ጥር 29 ቀን በዓመታዊ መታሰቢያ በዓላቸው ይከብራሉ፡፡ ማኅበረ ዴጌ ማለት የደጋጎች ሀገር ማለት ነው፡፡ የደጋጎች ሀገር የተባለበት ምክንያት ብዙ ሺህ ቅዱሳን ተሰብስበው ስለሚኖሩበት ነው፡፡ ገዳሙ የሚገኘው በትግራይ ክልል በአክሱም አውራጃ ከአክሱም ከተማ ወደ ደቡብ ምዕራብ በሚወስደው መንገድ አስራ ሁለት ኪሎሜትር ያህል ርቀት ላይ ነው፡፡

በቦታው ላይ ጥንት መሥዋዕተ ኦሪት ይሠዋበት ነበር፡፡ በኋላም በ40 ዓ.ም ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ወደ አገራችን በመጣ ጊዜ በቦታው ላይ ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አጥምቋል፡፡ በወቅቱ የነበረችው ንግሥትም በቅዱስ ማቴዎስ እጅ ተጠምቃለች፡፡ ቅዱስ ማቴዎስም ንግስቲቱን ካጠመቀ በኋላ ቀጥሎ መኳንንቱን፣ መሳፍንቱንና የጦር ሠራዊቱን ሁሉ አጥምቋቸዋል፡፡ ከዚህም በኋላ የጻድቃንን ማህበር አቋቁሞ በጌታችን ስም በየወሩ በ29 ቀን እየተሰበሰቡ ጽዋ እንዲጠጡ አድርጓቸው ወደ ኢየሩሳሌም ሄዷል፡፡

በ365 ዓ.ም በአስፍሕ ወልደ አብርሃም ንጉሰ ነገስት ዘኢትዮጵያ ዘመነ መንግስት ‹‹ሮምያ›› ከምትባል መንደር ቅዱሳን ‹‹ስለ ጽድቅ ብለው የሚሰደዱ ብፁአን ናቸው መንግስተ ሰማያት የነርሱ ናትና›› ያለውን ዳግመኛም ‹‹አባቱንና እናቱን ሚስቱንና ልጆቹን ያልተወ ሊያገለግለኝ አይችልም›› ብሎ ጌታችን የተናገረውን አስበው ቅዱሳን የዚህም ዓለም ጣዕም ጥቅም ንቀው ሀገራቸውን ትተው መንነው ወደ ኢትዮጵያ የመጡትን በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ነበሩ፡፡ እነዚህም ቅዱሳን በአክሱም ከተማ በስተሰሜን በሐውልቱ ጀርባ ቤተ ቀጠንት በሚባል ስፍራ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህል እንደ ተቀመጡ በዚያም ምቾትና ድሎት ስለተሰማባቸው ‹‹ለዚሁ ለዚሁማ ሀገራችንን ለምን ትተን መጣን? ስለዚህ ሱባዔ ገብተን በጾም በጸሎት ተወስነን የምንሄድበትን ቦታ በረከተ ነፍስ የምናገኝበትን ስፍራ እግዚአብሔር እንዲያሳየን እናመልክት›› ብለው ሱባዔ ገቡ ጾም ያዙ፡፡

ከሱባዔውም በኋላ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተገልጻላቸው ግማሾቹን እያንዳንዳቸው የሚኖሩበትን በዓት አመልክታቸው፣ በዚያም በጾምና በጸሎት ጸንተው እንዲኖሩ ነገረቻቸው፡፡ ሦስት ሺህ ያህሉን ደግሞ ከላይ ወደጠቀስነው ሥፍ ሄዱ፡፡ ከእነርሱ የተቀሩት ደግሞ ወደ ቆየፃ ሓባር፣ ተድባ፣ አኮርየን፣ ተንስሓ፣ ደብረ አንሳ ወደ ተባሉ ቦታዎች ሄደዋል፡፡ ተጨማሪ ሥስት ሺህ የሚሆኑት ደግሞ እዚያ ከነበሩት ጋር ተደመሩ፡፡ ከዚህም በኋላ እነዚህ ቅዱሳን ‹‹ከሁሉ ፍቅር ይበልጣል›› የሚለውን ጠብቀው በእምነት በፍቅር በአንድነት ጸንተው በየሳምንቱ እሁድ እሁድ ተዝካረ ሰንበትን ጠብቀው ማኅበር ይጠጡ ጀመር፡፡ በዚህም ጊዜ የማኅበረ ዴጌ ታሪክ ተቀየረ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአምሳለ ነዳይ ድሀ መስሎ በመካከላቸው ተገኘ፡፡ ግን ማንም አላወቀውም ነበር፡፡ ጌታችንም ከእነርሱ ጋር አንድ ማኅበርተኛ ሁኖ እንዲታወቅ ጠየቃችው፣ እነርሱም ፈቀዱለትና አንዱ የማኅበሩ አባል ሆነ፡፡ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ያህልም ከእነርሱ ጋር ሳይለይ ቆየ፡፡ በዚሁ ጊዜ ‹‹እስቲ ለእኔም ተራ ስጡኝ እንደአቅሜ ዝክር ላውጣ›› አላቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ድህነቱን አይተው ‹‹አይሆንም አንተ ድሀ ነህ፣ ከኛ ጋር ሁነህ በዓሉን አክብር እንጂ ምን አለህና ነው የምትደግሰው? ይቅርብህ›› አሉት፡፡ እርሱም ‹‹አይሆንም ስጡኝ እንጂ›› ብሎ ግድ አላቸው፡፡ እነርሱም ካልክማ ብለው ቀን ወስነው ሰጡት፡፡ ቀኑም ጥር 29 ነበር፡፡

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:48


ከማኅበርተኞቹ መካከል ‹‹ሳይዳ›› የሚባል ሰው ነበር፡፡ ይህም አሳላፊ ወይም ሙሴ ነበር፡፡ ይህም ሰው እንግዳና ድሀ ሰው ፈጽሞ አይወድም ነበርና ጌታችንም ከማኅበርተኞቹ መካከል ሲገኝ ድሀ መስሎ ስለነበር በጣም ይጠላው ነበር፡፡ ጌታችን አንድ ዓመት ከስድስት ወር ከእነርሱ ጋር ሲቀመጥም አንድ ቀን እንኳን አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ ሰጥቶት አያውቅም ነበር፡፡ የሆኖ ሆኖ መድረሱ አልቀረም የጌታችን ማኅበር ደረሰ፡፡ እንደማህበሩ ስርዓት የወይን ጠጅ የሚጠመቅባቸውን ጋኖች የሚያጥበው ሙሴው ወይም አሳላፊው ነው፡፡ ስለሆነም በሥርዓቱ መሠረት ጌታችን ሙሴውን ጠርቶ ጋኖችን እጠብልኝ አለው፡፡ አሳላፊውም በቁጣ ‹‹አንተ ቤትህ የማይታወቅ፤ ከየት አምጥተህ ማኅበር ልታደርግ ነው?›› አናንቆ አልታዘዝህም ብሎ ሄደ፡፡ ይህን የተመለከተው ጌታችንም አንድ እረኛ ጠርቶ ‹‹አንተ ልጅ ከብቶችህን እኔ እጠብቅልሃለሁና በዚህ ውሀ አምጣልኝ›› አለው፡፡ ትንሹ እረኛ ልጅም ገምቦውን ይዞ ትንሽ ወጣ እንዳለ ጌታችን ዘወትር በሚቀመጥበት ድንጋይ ላይ ሆኖ ዘንጉን ወደ ልጁ አቅጣጫ ወረወረው፣ ዘንጉንም ከልጁ ፊት ሂዶ ተተከለ፡፡ ልጁንም ጠርቶ ዘንጉንም እንዲነቅለው አዘዘው፡ ልጁም እንደታዘዘው ዘንጉን ቢነቅለው ውሀ ፈለቀ፡፡ ጌታችንም ‹‹ከእርሱ ቀድተህ አምጣልኝ›› አለው፡፡ ልጁም ከዚያ ውሀ ቀድቶ አመጣለትና ጋኖቹን አጠባቸው፡፡

በበዓሉ ቀን ማኅበርተኞቹ ‹‹ምን ሊያበላን ነው! ምንስ ሊያጠጣን ነው!›› ሳይሉ ሁሉም ተሰበሰቡ፡፡ ጌታችንም በፊታቸው ጋኖቹን ቢባርካቸው በተአምራት የወይን ጠጅ ሞልተው ተገኙ፡፡ ቀድቶ ቢሰጣቸውና ቢቀምሱትም በጣም ግሩም ጣፋጭ ስለነበር እጅግ አደነቁ፡፡ እነርሱም ጌታችንን ከጻድቃን አንዱ ስለመሰላቸው ከእግሩ ላይ ወድቀው ‹‹እስካሁን ድረስ ሳንበድልህ አልቀረንምና ይቅር በለን›› ብለው ለመኑት፡፡ እርሱም ‹‹ተነሱ›› ብሎ ካስነሣቸው በኋላ ‹‹እናንተ ምንም አልበደላችሁም፣ የጠየኳችሁን አድርጋችኋል የበደለኝ ግን አሳላፊያችሁ ነው፣ አንድም ቀን እንኳን አንድ ዋንጫ የወይን ጠጅ አልሰጠኝምና አፈራርዱኝ›› አላቸው፡፡ ነገር ግን ሙሴው ወይም አሳላፊው የማያፍር ደፋርና ርጉም ስለነበር ‹‹‹ይህ ሰው በልቶ አልበላሁም፣ ጠጥቶ አልጠጣሁም› የሚል ስለሆነና ስለማይጠግብ ነው እንጂ እንዲያውም ለእናንተ አንድ አንድ ዋንጫ ሲሰጣችሁ ለእርሱ ሁለት ሁለት ነበር የሚሰጠው›› ብሎ የሐሰት ቃል መለሰ፡፡ ጌታችንም በዚህ ጊዜ ‹‹እንግድያስ እኔ የጠጣሁበት ዋንጫ ትቅረብና ትመስክርብኝ›› አለው፡፡ በዚሁ ተስማምተው ሙሴው ሄዶ አንድ ሸራፋ ዋንጫ አምጥቶ ‹‹በዚህ ነበር የሚሰጠውና የሚጠጣው›› ብሎ አቀረበ፡፡ በዚህም ጊዜ ዋንጫዋ ከተቀመጠችበት አንድ ክንድ ከስንዝር ወደላይ ተነሥታ በሰው አንደበት በመመስከር ‹‹ዓለማትን የፈጠረ አምላክ ምስክሬ ነው እኔ የያዝኩትን የወይን ጠጅስ እርሱ በከንፈሩ አልነካኝም በሌሎቹ ሰዎች እጅ ግን ተይዤ ያየኝ ነበር›› አለች፡፡ ያንጊዜም ሙሴውን ሳይዳን እንደ ዳታንና እንደ አቤሮን ምድር ተከፈተችና ዋጠችው፡፡ ማኅበረ ጻድቃንም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑ ዐውቀው እንደገና ከእግሩ ወድቀው ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ለመኑት፡፡ ጌታችንም ‹‹ይቅር ብያችኋላሁ›› ካላቸው በኋላ ‹‹ስማችሁን የጠራ፣ በስማችሁ ተዝካር ያወጣ፣ ድኆችን የረዳ፣ ያለበሰ፣ ያጎረሰ፣ የመጸወተ፣ ቤተ ክርስትያን የሠራ ያሠራ እሰከ 14 ትውልድ ድረስ ምሬላችኋለሁ›› የሚል ድንቅ ቃል ኪዳን ገባላጣቸው፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህችን የተቀደሰች ቦታችሁን መጥቶ የተሳለመ ቢኖር ኢየሩሳሌምን እንደተሳለመ እቆጥርለታለሁ›› አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ‹‹እንደነ ሄኖክና ኤልያስ ከሞት ተሰወሩ›› ብሏቸው በማግሥቱ ጥር 30 ቀን ከዚህ ዓለም ሠውሯቸዋል፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ገብረ_ናዝራዊ

ዳግመኛም በዚህች እለት የከበሩ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ገብረ ናዝራዊ ዘቀወት አረፈ፡፡ ጻድቁ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በሰሜን ሸዋ ይፋትና ጥሙጋ ደብረ ሲና ውስጥ ቀወት በምትባለው ቦታ በ13ኛው መ/ክ/ዘ ተወለዱ፡፡ አባታቸው ስቡሐ አምላክ እናታቸው ክርስቶስ ክብራ የሚባሉ የነገሥታት ወገን ናቸው፡፡ የአባታችን የስማቸው ትርጉም ‹‹በስዕለት ለእግዚአብሔር የተሰጠ ልዩና የተቀደሰ ማለት ነው፤ ይህም የበኩር ልጅ ስለሆኑና በስዕለት የተሰጡ ስለሆነ ነው፡፡ ወላጆቻቸውም ፈሪሃ እግዚአብሔርንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በሚገባ እያስተማሩ በምግር በሃይማኖት ኮትኩተው አሳደጓቸው፡፡ ዲቁናን ከተወበሉ በኋላ በሸዋ አካባቢ እየተዘዋወሩ ወንጌልን መስበክ ጀመሩ፡፡ ነገር ግን በዚህ በሐዋርያዊ አገልግሎታቸው ጊዜ ብዙ ፈተና ገጠማቸው ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ከላይ በአቡነ ታዴዎስ ገድል ላይ እንዳየነው ሰይጣን በንጉሡ በዓምደ ጽዮን ፍቅረ ዝሙት አሳድሮበት በክፉዎችም ምክር አታሎት የአባቱን ሚስት በማግባቱ ምክንያት አቡነ ገብረ ናዝራዊም ይህን ሲሰሙ እንደ ነቢዩ ኤልያስና እንደ መጥምቁ ዮሐንስ በቀጥታ ሄደው ንጉሡን ገሥጸው አወገዙት፡፡ በዚህም ምክንያት ንጉሡ በማሠር ብዙ አሠቃያቸው፡፡ ጳጳሱ አባ ያዕቆብን ጨምሮ ብዙ ቅዱሳንም ለስደት ተዳረጉ፡፡

አቡነ ገብረ ናዝራዊም አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸው ከእሥር እንደተፈቱ ወደ ላሊበላ በመሄድ 12 ዓመታት በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ወደ ሐይቅ አቡነ ኢየሱስ ሞዐ ገዳምም በመሄድ ካገለገሉ በኋላ ወደ ትግራይ ሄዱ፡፡ ከዚያም ግብፅን አቋርጠው ወደ ኢየሩሳሌም ለመሄድ ከጳጳሱ አባ ያዕቆብ ጋር ሲነሡ አባ ያዕቆብ ‹‹በዓትህ ኢትዮጵያ ብቻ ናት›› ብለው ስለነገሯቸው ሀሳባቸውን ትተው የጳጳሱን ምክራቸውን ተቀበሉና ከጉዞአቸው ቀሩ፡፡

ከዚህም በኋላ ወደ አዲግራት በመሻገር ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን ፈጽሙ፡፡ መጀመሪያ እንደመጡ ያረፉባት አጋዝና በተባለቸው ተራራማ ቦታ ነበር፡፡ የአባታችን ሁለተኛ ቤተ ክርስቲያናቸው በዚህ ቦታ ላይ ታንጾ ይገኛል፡፡ በቦታውም ላይ 8 ዓመት ኖረውበታል፡፡ ወደሸለቆመም ዘቅዝቀው ወርደው ወደ ማየ ኢየሱስ በመሄድ ሓባ በምትባለው ተራራ ላይ የቁፋሮ ሥራ ጀምረው ባለ ሁለት ዓምድ የሆነ አንድ በር ያለው ቤተ ክርስቲያን አንጸው ሲያበቁ አሁን ወዳለው ገዳማቸው ደብረ ኀረይክዋ መጡ፡፡

አቡነ ገብረ ናዝራዊ ደብረ ኀረይክዋ ዓምባ ላይ ከወጡ በኋላ በመጀመሪያ የተለያየ መጠንና መጠሪያ ስም ያላቸውን ከዓለት ላይ የተፈለፈሉ አስደናቂ የሆኑ ከ44 በላይ የውኃ ጉድጓዶችን አንጸዋል፡፡ ከጉድጓዶቹም በተአምራት ጸበሎች ፈልቀውላቸዋል፡፡ እነዚህንም ጸበሎች እስከዛሬ ድረስ መጠናቸው ምንም ሳይጎድል ገዳማውያኑ ይጠቀሙባቸዋል፡፡ ጻድቁ በዚሁ ቦታ ከዓለት ላይ ፈልፍለው ያነጹት አስደናቂ ቤተ መቅደስ ይኛል፡፡ መካነ መቃብራቸውም በዚሁ ገዳማቸው ውስጥ በክብር ተቀምጦ ይገኛል፡፡

አቡነ ገብረ ናዝራዊ በጾምና በጸሎት ተወስነው ሕዝቡን በማስተማር ብዙ አስገራሚ ተአምራትን በመፈጸም ላይ እንዳሉ የቀድሞ ጓደኛቸው የነበሩትና በኋላም የነገሡት ዐፄ ዓምደ ጽዮን በትግራይ ከፍለ ሀገር አጋሜ አውራጃ ዓምባ ጽዮን በተባለው ተራራ ላይ ሽፍቶች ተነሥተው መሽገው ነበር፡፡ ንጉሡም እነዚህን የተነሡባቸውን ሽፍቶች ለመያዝ ክተት ሠራዊት ምታ ነጋሪት ብለው 10 ሺህ ሠራዊት ይዘው ወደ አካባቢው ዘመቱ፡፡ ንጉሡም በአካባቢው እንደደረሱ አቡነ ገብረ ናዝራዊ በዚያ እንዳሉ ስለሰሙ መልእክተኞችን ልከው አስመጧቸውና የመሸጉትን ሽፍቶች በምን ዓይነት ዘዴ ድል ማድረግ እንደሚችሉ የጠቋቸው፡፡ አቡነ ገብረ ናዝራዊም ‹‹ለሦስት ቀናት ያህል በቤተ ክርስቲያን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:37


ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን እህታችን እናመሰግናለን ያገልግሎት ዘመንሽን ይባርክልን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:31


ኸረ ተው አንድ ዝማሬ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:28


አሜንንንን🙏🙏🙏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:26


እስኪ እህት ወንድሞቼ አንድ ዝማሬ እግዚአብሔር እንድናመሰግነው ልቀቁልን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:19


በርቱልኝ የተዋሕዶ ቤተሰቦቼ በጣም ደስ ትላላችሁ በቤቱ በቃሉ ያፅናችሁ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:16


👏👏👏👏👏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Feb, 19:12


ሌላ የሚሳተፍ የለም ሰዓታችን እየሄደ ስለሆነ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

03 Feb, 11:05


ይህ ቻናል በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ስር በሚገኙ አብያተ ክርስትያናት ውስጥ የሚከበሩ ዓመታዊ የንግሥ በዓላትን የሚገልፅ ነው። 
 
የንግሥ በዓላት የት ደብር እንደሚከቡሩ የሚገልፅ ቻናል ይቀላቀሉን!
👇👇
📎 https://t.me/beale_nigs
📎 https://t.me/beale_nigs

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

03 Feb, 09:57


#ጥያቄ ✞✞✞
==========

5⃣.በብሉይ ኪዳን ሕግ ሰው ካለው ላይ ከአስር አንድ ይስጥ ይላል። ይህ ከአስር አንድ የምንሰጠው ምን ይባላል?

-----------------------------------------------

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

02 Feb, 18:28


4. በጥር 25 በዚህች ዕለት አባ ጴጥሮስ ያረፈበት ቀን ነበር:: ይህም ቅዱስ ምን ይሰራ ነበር
ሀ. ቀራጭ
ለ.  የእንጨት ስራ
ሐ.  እረኛ
መ. መልሱ አልተሰጠም

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

02 Feb, 18:14


3. ቅዱስ መርቆሬዎስ ሲወለድ የወጣለት ስም ማን ነበረ ?
ሀ. ፒሉፓዴር
ለ. ኖህ
ሐ. አስሊጥ
መ. መልሱ የለም

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

02 Feb, 17:50


2. ቅዱስ መርቆሬዎስ ማለት ምን ማለት ነው ?
ሀ. የአብ ወዳጅ
ለ. ኦርቶዶክስ
ሐ. የአብ ስጦታ
መ. መልስ የለም

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

02 Feb, 17:38


እንሳተፍ ቤተሰብ 🙏🙏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

02 Feb, 17:31


1, ጥር 25 በዚህች ዕለት ቅዱስ መርቆርዮስ በስዕሉ ላይ አድሮ የትኛውን ቅዱስ የረዳበት ዕለት ነበር?

ሀ. የቅዱስ ባስልዮስን 
ለ. ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐ. ቅዱስ ሰብስትያኖስ
መ. መልስ የለም

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Jan, 18:04


#ጥር_16

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን የከበረ
#ቅዱስ_ፊላታዎስ በሰማዕትነት ሞተ፣ የከበረ አባት ተጋዳይ የሆነ #ቅዱስ_ጰላድዮስ አረፈ፣ የከበረ አባት #አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የሶሪያ ሰው ሊቅ #ማር_ዳንኤል አረፈ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ፊላታዎስ_ሰማዕት

ጥር ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን የስሙ ትርጒም የእግዚአብሔር ወዳጅ የሆነ የከበረ ፊላታዎስ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ ከአንጾኪያ ሀገር ሰዎች ወገን ነው ወላጆቹም መረግድ የሚባል ላም ያመልኩ ነበር የተፈተገና የበሰለ በሰሊጥ ቅባትና በማር የተለወሰ ስንዴ ይመግቡታል ሁል ጊዜ ሦስት ጊዜ የተወደደ የሽቶ ቅባት ይቀቡታል የወይን ጠጅም ያጠጡታል ለክረምትና ለበጋም ማደሪያ አለው በአንገቱም የወርቅ ዛንጅርና ድሪ አለ።

ይህ ቅዱስ ፊላታዎስም መልኩ እጅግ የሚአምር ነበር ዐሥር ዓመትም በሆነው ጊዜ ለዚያ በሬ ይሰግድ ዘንድ ወላጆቹ ተናገሩት ሕፃን ፊላታዎስም ቃላቸውን አልሰማም እነርሱም እርሱን ስለሚወዱት ልቡን ሊያሳዝኑት ስለአልፈለጉ አላስገደዱትም።

የከበረ ፊላታዎስም ያን ጊዜ ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን አያውቀውም ነበር ፀሐይም አምላክ ይመስለው ነበር በፀሐይም ፊት ቁሞ እንዲህ አለ አንተ ፀሐይ አምላክ ከሆንክ ታስረዳኝ ዘንድ እለምንሃለሁ አለው። በዚያንም ጊዜ ከወደላይ እንዲህ የሚል ቃል ወደርሱ መጣ እኔ አንተ ልታወቀውና ስለ ከበረ ስሙ ደምህ ይፈስ ዘንድ ያለህ አምላክ አይደለሁም።

ሕፃን ፊላታዎስም ይህን በሰማ ጊዜ ልቡ ጸና ዳግመኛም በዚያች ሰዓት ወደርሱ መልአክ ተላከ እርሱም የአምላክን ምሥጢር አስረዳው የሚነግረውንም ያስተውል ዘንድ ልቡናውን ከፈተለት ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ክርስቶስ ሰው እስከሆነበት ድረስ የሆነውን ይነግረው ጀመረ በልቡናውም እጅግ ደስ አለው።

ከዚያችም ዕለት ወዲህ ሁል ጊዜ አብዝቶ የሚጾምና የሚጸልይ ሆነ ከብቻው እንጀራና ጨው በቀር አይበላም ለድኆችና ለምስኪኖችም ምጽዋት ይሰጣል።

ከዓመትም በኋላ ወላጆቹ አሰቡ ለልጃቸው ባልንጀሮች ምሳ አዘጋጁ ሳይበሉና ሳይጠጡ አስቀድሞ ልጃቸው ፊላታዎስ ለዚያ በሬ ዕጣን እንዲአሳርግ ፈለጉ ሕፃኑ ፊላታዎስም በበሬው ፊት ቁሞ ሰዎች የሚያመልኩህ አንተ በእውነት አምላክ ነህን አለው።

ያን ጊዜ ከበሬው እንዲህ የሚል ቃል ወጣ እኔ አምላክ አይደለሁም ሰይጣን በእኔ ላይ አድሮ ሰዎችን እንዳስት አደረገኝ እንጂ ይህንንም ብሎ ያ በሬ ተነሥቶ የቅዱስ ፊላታዎስን ወላጆች በቀንዶቹ ወግቶ ገደላቸው ፊላታዎስም ያንን በሬ ይገድሉት ዘንድ አመድ እስከሚሆንም በእሳት አቃጥለው በነፋስ ይበትኑት ዘንድ አገልጋዮቹን አዘዛቸው እርሳቸውም እንዳዘዛቸው አደረጉ።

የወላጆቹም በድኖቻቸው ወድቀው ነበር እግዚአብሔርም ጸጋውን አሳድሮበታልና ቅዱስ ፊላታዎስ በወላጆቹ በድኖች ላይ ጸለየ ነፍሳቸውም ተመልሳ በዚያን ጊዜ ተነሡ በሲዖልም ከአዩት ሥቃይ ነገሩት። ከዚህም በኋላ ቅዱስ ፊላታዎስና ወላጆቹ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም የክርስትና ጥምቀትን ተጠመቁ ሀብተ ፈውስም ተሰጥቶት በጸሎቱ በሽተኞችን የሚፈውስ ሆነ።

ወሬውም በንጉሡ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ ተሰማ መልከተኞችንም ልኮ ወደርሱ አስቀረበውና ለአጵሎን ዕጣን ያሳርግ ዘንድ አዘዘው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት ባልሰማውም ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ። በአላንጋዎች ገረፉት በሆዱም ላይ የሚከብዱ ደንጊያዎችን አደረጉ እርሱ ግን በክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል የጸና ነው።

ከዚህም በኋላ ንጉሡንና የረከሱ አማልክቶችን ሊረግማቸው ጀመረ ንጉሡም አፉን ይመቱት ዘንድ ምላሱንም ይቆርጡ ጥርሶቹንም ይሰብሩ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ያለ ጥፋት ጤነኛ አደረገው።

ከዚህም በኋላ ንጉሡ ይሸነግለው ዘንድ መልካም ቃል ሊናገረው ጀመረ የከበረ ፊላታዎስ ግን ሲዘብትበት ለጣዖቶቹ እንደሚሠዋ ቃል ገባለት ንጉሡም እውነት ስለመሰለው ደስ አለው አጵሎንንና አገልጋዮቹን ለጠዖትም የሚገዙትን ሁሉንም እንዲአመጡአቸው አዘዘ ዳግመኛም በከተማው ውስጥ ዓዋጅ ነጋሪ ይዞር ዘንድ አዘዘ እንዲህ እያለ ሁላችሁ አሕዛብ ኑ ፊላታዎስ ለአማልክት ሲሠዋ ታዩ ዘንድ አሕዛብም ሁሉ ወደ ፍርድ አደባባይ ተሰበሰቡ።

ጣዖታቱንም በጐዳና ውስጥ ሲያመጡአቸው የከበረ ፊላታዎስ የክብር ባለቤት ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ጣዖታቱንና አገልጋዮቻቸውን ጣዖተ አምላኪዎችንም ሁሉንም ምድር አፍዋን ከፍታ ትውጣቸው ዘንድ ለመነው ዋጠቻቸውም። በአደባባዩም ውስጥ ታላቅ ጩኸትና ሽብር ሆነ። ይህንን ድንቅ ሥራ አይተው ብዙዎች በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ንጉሡም ተቆጥቶ ራሳቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ቆረጡአቸውም የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀብለው ወደ ዘላለም ሕይወት ገቡ።

የከበረ ፊላታዎስንም ማሠቃየቱን ንጉሡ በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባ_ዸላድዮስ_ገዳማዊ

በዚህችም ቀን የከበረ አባት ተጋዳይ የሆነ ጰላድዮስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከዋሻው ሳይወጣ የሴቶችን ፊት ሳያይ ሃምሳ ዓመት ኖረ ድንቆች ተአምራቶችን የማድረግና የትምቢት መናገር ሀብት ተሰጠው ዜናውም በቦታው ሁሉ ተሰማ።

በምስር አገር አንድ ነጋዴ ነበር ይነግድም ዘንድ በመርከብ ተጭኖ ሔደ ማዕበልም ተነሥቶበት ለመሥጠም ደረሰ በአባ ጰላድዮስ ጸሎት ተማጽኛለሁ ከሞት ከዳንኩ መቶ የወርቅ ዲናር ለእርሱ እሰጣለሁ ብሎ ጮኸ በዚያንም ጊዜ በመስቀሉ መርከቡን ሲቀዝፍ አባ ጰላድዮስን አየው ወደ ወደብም አደረሰው።

ከዚህም በኋላ ወደ አገር ውስጥ በደረሰ ጊዜ ያ ነጋዴ ፈረስ ተከራይቶ ያንን መቶ የወርቅ ዲናር ይዞ ወደ አባ ጰላድዮስ ሔደ በመሸም ጊዜ በአንዲት አገር በእንግዳ ማደሪያ ውስጥ አደረ። በዚያም ሞሪት የሚባል ሰው አግኝቶ በልቡ ያለውን ሁሉ ምሥጢሩን ነገረው ሞሪትም እኔ ቦታውን አውቀዋለሁና ወደርሱ አደርስሃለሁ አለው በማግሥቱም ሁለቱም ወደ አባ ጰላድዮስ ሔዱ በደረሱም ጊዜ ሰላምታ ሰጡት ነጋዴውም ያን ያመጣውን ወርቅ ሰጠው። አባ ጰላድዮስም አይቶ ባረከው እንዲህም አለው ወደዚህ ወርቅ ፍላጎት የለኝም ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ጠቃሚ እንዲሆንህ ሒደህ ለድኆችና ለችግረኞች በትነው አለው ነጋዴው ግን ይቀበለው ዘንድ ከእግሩ ሥር ወድቆ ማለደው ጥቂትም ወሰደለትና እንዲህ አለው ለበረከት ይህን ተቀብየሃለሁ የቀረውን እንዳዘዝኩህ አድርገው አለው።

ነጋዴውም ወርቁን ይዞ ተመለሰ ከተራራውም ወርዶ ከወንዝ ደረሰ በዚያንም ጊዜ ሰይጣን በሞሪት ልብ አደረና ገንዘቡን ሊወስድ ወደደ በአደገኛነትም በላዩ ተወርውሮ ገደለው በሌሊትም በድኑን ተሸክሞ ወስዶ ከአባ ጰላድዮስ ደጅ ጣለው በማግሥቱም ወደ አገረ ገዥ ሒዶ ስለ ሟቹ ነገረው።

መኰንኑም ወደዚያ በደረሰ ጊዜ አባ ጰላድዮስን ይዞ ጽኑ እሥራትን አሠረውና ስለ ሞተው ሰው ሊመረምረው ጀመረ። እርሱም እኔ አልገደልኩም አለው ወደሞተውም ቀርቦ ቃሬዛውን ይዞ ረጅም ጸሎትን ጸለየ በድን ሆይ ማን እንደገደለህ ተነሥተህ ትናገር ዘንድ በእግዚአብሔር ስም አዝዝሃለሁ አለ ወዲያውኑ የሞተው ተነሥቶ ስለ ገንዘቡ ሞሪት እንደ ገደለው ተናገረ መኰንኑም ይህን ድንቅ ተአምር በአየ ጊዜ ደነገጠ ለአባ ጰላድዮስም ሰገደለት በላዩም ክፉ ስላደረገ ተጸጸተ ሞሪትንም ሊገድለው ወደደ አባ ጰላድዮስም አስተወው። ከብዙ ተጋድሎም በኋላ እግዚአብሔርን ደስ አሰኝቶ አገልግሎ በመልካም ሽምግልና አረፈ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

19 Jan, 19:51


#ጥር_12

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም

ጥር ዐሥራ ሁለት በዚችህም ቀን የክብር ባለቤት ጌታ #በቃና_ዘገሊላ ለሰራ ተአምር መታሰቢያ ነው፣ የመላእክት አለቃ #ቅዱስ_ሚካኤል_ቅዱስ_ያዕቆብ_እሥራኤልን የረዳበት ነው፣ ኃይለኛ የሆነ #ቴዎድሮስ_በናድሌዎስ በሰማእትነት ሞተ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቃና_ዘገሊላ

ቃና ዘገሊላ በቀጥታ ትርጉም የገሊላዋ ቃና ማለት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ በጥምቀት በዓል ማግስት(ጥር 12) ቀን የቃና ዘገሊላ በዓል ይከበራል፡፡ ይህ በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በድምቀት የሚከበር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ ያለው በዓል ነው፡፡ በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍል በምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈፀመው ተአምር መነሻነት ነው፡፡
የቃና ዘገሊላ ጥንተ ነገሩ ወይም ታሪኩ የተፈፀመው የካቲት 23 ቀን ነው፡፡ ነገር ግን አባቶቻችን የውኃን በዓል ከውኃ በዓል ጋር ለማክበር ብለው የየካቲቱን በዓል ወደ ጥር 12 አምጥተውታል፡፡ ይህም ውኃ ወደ ወይን የተለወጠበትን በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ለማስተሣሠር ለማስኬድ ነው፡፡ በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር 12 ቀን ይከበራል፡፡

በቃና ዘገሊላ ምን ተፈፀመ?

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በምትሆን በቃና በተደረገ ሠርግ ላይ ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር ተገኝቶ ነበር፡፡ ‹‹ወሀለወት ህየ እሙ ለእግዚእ ኢየሱስ›› ‹‹የጌታ የኢየሱስ እናትም በዚያ ነበረች›› እንዳለ ቅዱስ ዮሐንስ በወንጌሉ (ዮሐ 2÷1) እመቤታችን ለሠርገኞቹ ዘመድ ነበረችና ከልጇ ከወዳጇ ከኢየሱስ ክርስቶስ በሰርጉ ላይ ታድማ ነበር፡፡ እናትን ጠርቶ ልጅን መተው ሥርዓት ስላልሆነ፤ በተጨማሪ ደግሞ ደቀ መዛሙርቱ ከጌታ ጋር በሰርጉ ታድመዋል፡፡ ይህም መምህርን ጠርቶ ደቀ መዛሙርቱን መተው ሥርዓት ስላልሆነ (ተገቢ ስላልሆነ) ነው፡፡ የሠርጉ ሥነ-ሥርዓት በሠመረ ባማረ ሁኔታ እየተከናወነ ሳለ ድንገት የወይን ጠጅ አለቀ፡፡ አስተናባሪዎቹ በጭንቀት ባሕር ሰጥመው ምን እንደሚያደርጉ ግራ በገባቸው በጠበባቸው ጊዜ የችግር ጊዜ ደራሽ የኃዘን ጊዜ አፅናኝ የሆነችው የአምላክ እናት ድንግል ማርያም ቅዱስ ገብርኤል እንደተናገረ በፀጋ የተሞላች ናትና (ሉቃ 1÷28) ማንም ሳይነግራት የልቦናቸውን ጭንቀት አይታ፣ ጎዶሎአቸውን ተመልክታ ወደ ልጇ ወደ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘወር ብላ ‹‹ወይንኬ አልቦሙ›› ‹‹ወይን ጠጅ እኮ አልቆባቸዋል›› አለችው፡፡ እርሱም መልሶ ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› ‹‹ጊዜዬ ገና አልደረሰም›› አላት፡፡ እመቤታችንም ለአገልጋዮቹ ‹‹የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ›› አለቻቸው፡፡ ጌታም በቦታው የነበሩ ስድስት ጋኖች ውኃ ሞልተው እንዲያመጡ አዘዛቸው፡፡ ውኃውንም ወደ ወይን ለውጦ ለሊቀ ምርፋቅ (ለአሳዳሪው) እንዲሠጡት አዘዘ፡፡ አሳዳሪውም ወደ ወይን የተለወጠውን ውኃ በቀመሰ ጊዜ አደነቀ፡፡ ከወዴት እንደመጣ ስላላወቀ ሙሽራውን ‹‹ሰው ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን የወይን ጠጅ ያቀርባል ከሰከሩም በኋላ መናኛውን ያቀርባል አንተ ግን መልካሙን እስከ አሁን አቆይተሃል›› አለው፡፡ ወይኑም በሰው እጅ ያይደለ በሠማያዊው አባት የተዘጋጀ ስለነበር ጣፋጭ እና ልብን የሚያስደስት ነበር፡፡

‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?››

ይህንን የጌታችንን ንግግር ብዙዎች በዘመናችን ሲሣሣቱበት ይታያል ፡፡ ክብር ይግባውና አምላካችን ይህንን የተናገረው እናቱን ሊያቃልል ሽቶ አይደለም፡፡ ስለሆነም ከመጽሐፍ ቅዱስ አንፃር ይህን አረፍተ ነገር መመልከቱ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ በተናጠል ስንመለከት ‹‹አንቺ ሴት›› ሴት የሚል ቃል የፆታ መጠሪያ ነውና በፆታዋ አክብሮ ሲጠራት ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሔዋን ከአዳም በተፈጠረች ጊዜ አዳም እንዲህ ሲል ተናግሮ ነበር ‹‹ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት ሥጋም ከሥጋዬ ናት እርስዋ ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል›› (ዘፍ 2÷23) በመሆኑም ጌታ አንቺ ሴት ማለቱ ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍስዋ ነፍስ መንሣቱን ለማጠየቅ ነው፡፡ ‹‹ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› የሚለውን ዐረፍተ ነገር የንቀት ስለመሰለን ብቻ ‘ የዳቦ መልክ የያዘ ድንጋይ፤ ዳቦ ነው እንደማይባል’ የንቀት ንግግር ነው ልንል አይገባም፡፡ ጌታም እንዲህ ሲል ውኃውን ወይን አድርግላቸው ብትይኝ አላደርግም እልሽ ዘንድ ከአንቺ ጋር ምን ፀብ አለኝ ማለቱ ነው፡፡ ይህ ንግግር በመጽሐፍ ቅዱስ በብዙ ቦታ ተጽፎ እንደሚገኘው በዕብራውያን ዘንድ የተለመደ የአነጋገር ዘይቤ ነው፡፡ለአብነት ይሆን ዘንድ ጥቂት ጥቅሶችን ከመጽሐፍ ቅዱስ እንመልከት፡-

የሰራፕታዋ ሴት በ 1ነገ 17÷18 ላይ እንደምናገኘው ልጇ በሞተባት ጊዜ ኤልያስን በሐዘን በለቅሶ እንዲህ ብላ ነበር ‹‹የእግዚአብሔር ሰው ሆይ ከአንተ ጋር ምን አለኝ?›› ትወልጃለሽ ብለህ የወለድኩት ልጅ ምን በድዬህ ምንስ አስከፍቼህ ሞተብኝ? ስትል ነው እንጂ አባባሏ የንቀት ወይም የማቃለል አይደለም፡፡

በጌርጌሴኖን አንድ አጋንንት ያደረበት ሰው ወደ ጌታችን ቀርቦ ‹‹የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ከአንተ ጋር ምን አለኝ?›› አለው፡፡ እውነት ይህ ቃል የንቀት ይመስላልን? የልዑል እግዚአብሔር ልጅ ብሎ አምላክነቱን እየመሰከረ ሊያቃልለው ይችላልን? ደግሞስ ላለመጥፋት ፍፁም የሚፈልግ ሰው ሊያድነው ሥልጣን ያለውን ሊንቅ ይችላልን? አይችልም፡፡ ይህ ቃል የሚያመለክተው ምን አጠፋሁ ስለምን ልታጠፋኝ ወደድክ በማለት መፍራት መራዱን ነው፡፡ (ሉቃ 8÷28-29) ስለሆነም ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› የሚለው የንቀት አለመሆኑን ከሁለቱ ጥቅሶች መረዳት እንችላለን፡፡ እመቤታችን እና ጌታ በንግግር አልተቃረኑም ንግግራቸው የፍቅር ነበር፡፡ ንግግራቸው የመግባባት ስለነበር ነው ‹‹አንቺ ሴት ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?›› ካላት በኋላ ዘወር ብላ አገልጋዮቹን የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ ያለችው፡፡

‹‹ጊዜዬ አልደረሰም›› ጌታ ይህን ቃል የተናገረው ስለ ብዙ ምክንያቶች ነው፡፡ ጊዜዬ አልደረሰም ማለቱ፡-

እግዚአብሔር ነገሮችን የሚያከናውንበት የራሱ ጊዜ አለው፡፡ በመሆኑም ይህን ተአምር የምፈፅምበት ጊዜዬ አልደረሰም ሲል ነው፡፡

አንድም ጋኖቹ ውስጥ የቀረ ወይን ስለነበረ ባለው ላይ አበርክቶ እንጂ ውኃውን ወደ ወይን አልለወጠውም እንዳይሉ ወይኑ ከጋኑ ተንጠፍጥፎ እስኪያልቅ ድረስ ጊዜዬ አልደረሰም አለ፡፡

አንድም ይሁዳ ከሠርግ ቤት ወጣ ብሎ ነበርና ወደ ሠርግ ቤቱ እሰኪመለስ ጊዜዬ አልደረሰም አለ፡፡ ይሁዳ በቃና የገለጠውን ምስጢር ለእኔ ስላላሣየኝ ተከፍቼበት ከተአምራቱ ቢያጎድለኝ በሞቱ ገባሁበት፤ ሸጥኩት እንዳይል ምክንያት ለማሳጣት እንዲህ አድርጓል፡፡

አንድም እውነተኛ የሕይወት ወይን የሆነውን ደሜን የምሠጥበት ጊዜ ገና ነው ሲል፡፡

የድንግል ማርያም አማላጅነት በገሊላ ቃና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሠርግ ቤት ሣለ የወይኑን ማለቅ የማይመለከት ሆኖ አይደለም፡፡ ነገር ግን የእናቱን የድንግል ማርያምን አማላጅነት ሊገልጥ ስለወይኑ ማለቅ እስክትነግረው ድረስ አንዳች ነገር አላደረገም፡፡ ኋላ ግን የጭንቀት አማላጅ ድንግል ማርያም ስለ ወይኑ አሰበች ልጇ ወዳጇን ለመነች፡፡ እርሱም የእናቱን ልመና ተቀብሎ ተአምራቱን ፈፀመ፡፡ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሣይነግሯት በልብ ያለውን የምታውቅ የምትመረምር እናት ናትና የሠርጉ አስተናባሪዎች ይሄ ጎደለ ሣይሏት

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

19 Jan, 19:51


የልቦናቸውን ሐዘን ተመልክታ ከልጇ ከወዳጇ አማልዳ የጎደላቸውን ሞልታለች፡፡ያስጨነቃቸውንም አርቃለች፡፡ በችግራቸው ደርሳላቸዋለች፡፡ ታዲያ ሳይነግሯት የልቡናን አይታ ከማለደች ስሟን ጠርተው ለሚለምኗትማ እንዴት አብልጣ አታማልድ?

(ቅዱስ እንጦንስ መንፈሳዊ ማህበር ብሎግ)

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ያዕቆብ_እሥራኤል

በዚህች ቀን የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው በዚች ቀን እስራኤል ወደ ተባለ ያዕቆብ እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳውም ፈርቶ ሳለ አዳነው። ዮርዳኖስንም አሻግሮት ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሔደ።

እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያንና ራኄልን አጋባው ከዚህም በኋላ ከብዙ ገንዘቡና ከልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው ስለዚህም የሊቀ መላእክት ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ሆነ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ቴዎድሮስ_በናድሌዎስ

በዚህችም እለት የምስራቅ ሰው ፅኑእ ኃይለኛ የሆነ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ በሰማእትነት ሞተ።ይህም ታላቅ ተጋዳይ ከአንፆኪያ አገር ሰዎች ከመንግስት ወገን ነው የአባቱ ስም ሲደራኮስ ይባላል ለንጉሱም የጭፍራ አለቃ ነው የእናቱም ስምበጥሪቃ ይባላል ትርጓሜውም እመቤት ማለት ነው።

ንጉስ ኑማርያኖስም በጦርነት ውስጥ በሞተ ጊዜ ልጂ ዮስጦስም በጦርነት ውስጥ ነበር መንግስትም ያለ ንጉስ ነበረች የቴዎድሮስ አባት ሲድራኮስና ፋሲለደስ ዲዮቅልጣኖስ ነግሶ ሀይማኖቱን እስከ ካደ ድረስ የመንግስቱን አስተዳደር ይመሩ ነበር።

እርሱም ዲዮቅልጥያኖስ አስቀድሞ ከላየኛው ግብፅ የሆነ የዮስጦስ እኅት የንጉስ ኑማርዮስ ልጅ ሚስት ሆነችውና አነገሰችው ።ቅዱስ ቴዎድሮስም በአደገ ጊዜ በጦርነት ውስጥ ፈፅሞ ኃይለኛ ሆነ እርሱ ቅዱስ ቴዎድሮስ በሚሄድበት ጦርነት ሁሉ ጠላቶቹን ድል አድርጎ ያሳድዳቸዋል የፋርስ ሰዎችም ቴዎድሮስ ወደእናንተ መጣ ሲሏቸው ልባቸው ይሰበራል ይገዙለታልም ከእነርሱም ውስጥ ቴዎድሮስ የሮማውያን አምላክ ነው የሚሉ አሉ።

ለዲዮቅልጥያኖስ ክህደት ምክንያት የሆነ የቁዝ ንጉስን ልጅ ኒጎሚዶስን ሁለት ጊዜ የማረከው እርሱ ነው ከአባ አጋግዮስም ዘንድ በአኖረው ጊዜ አጋግዮስ በኒጎሚዶስ ክብደት ልክ ወርቅ አስመዝኖ ከቁዝ ንጉስ ተቀበሎ ወደ አባቱ መልሶታልና።

የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም በጦርነት ቦታ ቡናቢስ በሚባል ወንዝ አጠገብ ሳለ ስሙ ለውንድዮስ የሚባል ወዳጅም ሳለ ከዚህም በኃላ በአንዲት ሌሊት ራእይን አየ ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ መሰላል አለ። በላዩም በታላቅ ዙፋን ጌታችን ተቀምጧል በዙሪያውም የብዙ ብዙ አእላፍ መላእክት ያመሰግናሉ ከበታቹም ታላቅ ከይሲ ነበረ በዙፋኑ ላይ የተቀመጠውም ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሆይ ከኔ ልጄ ልትሆነኝ ትወዳለህን አለው።

ቴዎድሮስም አቤቱ አንተ ማነህ አለ ጌታችንም እኔ የአብ አካላዊ ቃል ኢየሱስ ነኝ ለአንተም ስለ ስሜ ደምህ ይፈስ ዘንድ አለህ አለው። በዚያንም ጊዜ ከቆሙት አንዱ ወሰደውና በእሳት ባህር ሶስት ጊዜ አጠመቀው ሁለመናውም በመንበሩ ዙሪያ እንደቆሙት ሆነ።

ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ጌታችንን ከወዳጄ ከለውንድዮስ መለየት አልሻም አለው ጌታም እንዲህ ብሎ መለሰለት እርሱ ብቻ አይደለም ለቁዝ ሰራዊት መኮነን የሆነ ኒቆሮስም ነው እንጂ።

ከዚህም በኃላ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ አየ እነዚያ መላእክትም ለውንድዮስንና ኒቆሮስን አመጠቋቸው ከእሳት ባህር ውስጥ አጠመቋቸውና እነርሱን ለቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሰጡት ከእንቅልፉም በነቃ ጊዜ ራእይን እንዳየ ለለውንድዮስ ነገረው ፈፅሞ ደስ ብሏቸው ተሳሳሙ።

ከዚህም በኃላ የቁዝ የሰራዊት አለቃ ኒቆሮስ ወዳለበት የእግዚአብሄር ኃይል ተሸከመቻቸው እርሱም በደስታ ተቅብሎ አስቀድሞ እንደሚያውቃቸው አቅፎ ሳማቸው እንርሱም እንዳዪት ያንን ራእይ ነገራቸው እጅግም አደነቁ ኒቆሮስም ቴዎድሮስ በናድሌዎስን እኔንና ወንድሜ ለወንድዮስን ለአንተ በእጅህ እንደሰጡን ወንድሜ ሆይ እወቅ አለው።

ከዚህም በኃላ በዚያን ጊዜ ወደ ሰራዊቶቻቸው መጡ በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ስሙ ደማቸውን ሊአፈሱ ተስማሙ።ከንጉሰ ቁዝ እንዴት እርቅ እንዳደረገ ሊጠይቀው ያን ጊዜ ንጉስ ወደ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ላከ ድዮቅልጥያኖስ ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን ክዶ ጣኦታትን በአመለከ ጊዜ ስለዚህ የቁዝ ሰዎች እጅግ ደስ ብሏቸዋልና።

የከበረ ቴዎድሮስ በናድልዮስም ሰራዊቱን ነፍሱን ከሰይፍ ሊያድን የሚወድ ወደ ፈለገው ይሂድ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ግን መጋደልን የሚሻ ከእኛ ጋር ይኑር አላቸው።

ሁሉም በታላቅ ድምፅ አንተ የምትሞትበትን ሞት እኛ ከአንተ ጋራ እንሞታለን አምላክህም አምላካችን ነው ብለው ጪሁ የተመሰገነ ቴዎድሮስም ዳግመኛ ነገራችሁ እውነት ከሆነ ሁላችሁም ወደዚህ ወንዝ ወርዳችሁ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሶስት ጊዜ ተጠመቁ አላቸው።

በዚያንም ጊዜ ልብሳቸውን አውልቀው ወደ ወንዙ ወርደው እንዳላቸውም ተጠመቁ ከውኃውም ሲወጡ ከሰማይ እንዲህ የሚል ቃልን ሰሙ ምስክሮቼ በርቱ ፅኑ አሸናፊዎችም ሁኑ እኔ ከናንተ ጋር እኖራለሁና።

የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ወደ አንፆኪያ ከተማ አቅራቢያ በደረሰ ጊዜ ሰራዊቱን ከከተማ ውጭ ትቶ ከሁለቱ ወዳጆቹ ከለውንድዮስና ከኒቆሮስ ጋር ገባ ንጉስም በክብር ተቀበሎ ስለ ጦርነት ወሬ ስለ ሰራዊቱም ጠየቀው እርሱም የሆነውን ሁሉ ነገረው።

ከዚህም በኃላ ለአጶሎን ስለ መስገድ አወሳ የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ንጉሱን ገሰፀው ዘለፈውም እንዲሁም ወዳጆቹ ለውንድዮስና ኒቆሮስ ንጉሱን ረገሙት እርሱም ተቆጣ ለውንድዮስንና ኒቆሮስን ወደ ሚዶን አገር ወስደው በዚያ ያሰቃዩአቸው ዘንድ አዘዘ።

ኒቆሮስ የፋርስ ሀገር የሰራዊት አለቃ መኮንን ስለነበረ ከፋርስ ሰዎች የተነሳ ዲዮቅልጣኖስ ፈርታልና በዚያም ለውንድዮስንና ኒቆሮስን በአሰቃዩአቸው ጊዜ በዚች ቀን ጥር አስራ ሁለት የሰማእትነት አክሊልን ተቀበሉ።

የከበረ ቴዎድሮስ በናድሌዎስን ግን ኮሞል በሚባል ታላቅ እንጨት ላይ አስተኝተው ቁጥራቸው መቶ ኃምሳ ሶስት በሆኑ በረጃጅም የብረት ችንካሮች እንዲቸነክሩት አዘዘ። እግዚአብሄርም መልአኩን ሚካኤልን ወደርሱ ልኮ በመከራው ሁሉ አፀናው።

በዚያንም ጊዜ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለፀለትና የመረጥኩህ ቴዎድሮስ ሆይ ሰላም ይሁንልህ ይህን ሁሉ መከራ ስለ ስሜ ታግሰሃልና ብፁእ ነህ ይህን ከሀዲ ንጉስ ታሳፈረው ዘንድ እሊህን ብርቶች ከስጋህ ውስጥ አውጥቼ እንዳድንህ ትሻለህን አለው።

ቴዎድሮስ በናድሌዎስም ጌታችንን እንግዲህስ ስለ ከበረ ስምህ መሞት ይሻለኛል አለው። ሁለተኛም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጄ ቴዎድሮስ በናድሌዎስ ሆይ እነሆ ሶስት አክሊላትን አዘጋጅቼልሀለሁ አንደኛው ስለ ድንግልናህ ሁለተኛው የዚህን አለም ክብር ትተህ መከራ ስለመቀበልህ ሶስተኛው ስለ ስሜ ደምህን ስለ አፈሰስክ ነው።አለው።

እኔም ቃል ኪዳንን ሰጠሁህ ስምህን ለሚጠራና መታሰቢያህን ለሚያደርግ በሁሉ ቦታ ከመከራው ሁሉ አድነው ዘንድ ለድኆችም ምፅዋት የሰጠውን ስለ አንተ በቤተ ክርስቲያን መባ ያገባውን የገድልህን መፅሀፍ የፃፈውንና ያፃፈውን ቤተ ክርስቲያንህንምየሰራውን ሁሉንም ኃጢአቱን ይቅር ብዬ መንግስተ ሰማያትን አወርሰዋለሁ። ጌታችንም ይህን ቃል ኪዳን ከሰጠው በኃላ ወደ ሰማይ አረገ ቴዎድሮስም ሶስቱን መላእክት አየ በዚያንም ጊዜ የከበረች ነፍሱን በእግዚአብሄር እጅ ሰጠ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

19 Jan, 19:33


💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕

[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛

🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

18 Jan, 19:54


✝️ #ጥር_11 ✝️

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር አስራ አንድ በዚች ቀን የክብር ባለቤት
#ጌታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ ተጠመቀ፣ የከበረ #እንጣልዮስ በሰማእትነት ሞተ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ #አባ_ዮሀንስ አረፈ፣ የከበረ ተጋዳይ ለሆነ አባት #አባ_ወቅሪስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#በዓለ_ጥምቀት (#በዓለ_ኤዺፋንያ)

ጥር አስራ አንድ በዚች ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአጥማቂው ዮሀንስ ዘንድ በዮርዳኖስ ወንዝ ውኃ ተጠመቀ።

ይችም እለት በዮናኒ ቋንቋ ኤጲፋንያ ትባላለች ትርጓሜውም "መለኮት የተገለጠበት ማለት ነው። "ልዩ የሆነች የሶስትነቱን ምስጢር ገልጦባታልና አብ ከሰማይ ሆኖ የምወደው በርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት እያለ ሲመሰክር ወልድም በዮርዳኖስ ወንዝ ቁሞ ሳለ መንፈስ ቅዱስም በነጭ ርግብ አምሳል በወልድ ራስ ላይ ሲቀመጥ ይህ አጥማቂው ዮሀንስ እንደመሰከረ።

እንዲህ ሲል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠምቆ ከውኃ በወጣ ጊዜ ወዲያውኑ ሰማይ ተከፈተ መንፈስ ቅዱስም በርግብ አምሳል ወረዶ በጌታችን ራስ ላይ ተቀመጠ ከሰማይም እንዲህ የሚል ቃል መጣ ይህ የምወደው በእርሱ ደስ የሚለኝ ልጄ ነው እርሱንም ስሙት።

በዚች እለት ጌታችን ራሱን ገልጦአልና ከዚህ በፊት ሰላሳ አመት ያህል ራሱን አልገለጠም ነበር ግን በዚች እለት ለእስራኤል ልጆች ራሱን ገለጠ እነሆ የእግዚአብሔር በግ የአለምን ኃጢአት የሚያስወግድ ብሎ መጥምቁ ዮሀንስ እንደገለጠው የከበረ ወንጌል ምስክር ሆነ።

እኔ አላውቀውም ነበር ነገር ግን እስራኤል ያውቁት ዘንድ በውኃ ላጠምቅ ስለዚህ መጣሁ አለ። በዚህም በዓል የእግዚአበሄር ልጅ የክርስቶስ የጌትነቱ ክብር ተገልጧል እርሱም የአለሙን ሁሉ ሀጢአት ለማስወገድ የሚሰዋ የእግዚአብሔር አማናዊ በግ ነው።

ስለዚህም ይህ በዓል በክርስቲያን ወገኖች ሁሉ ዘንድ የከበረና ከፍ ከፍ ያለ ሆነ በርሱም የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በጥምቀቱ በአከበረው ውኃ ይነፁበታል የተቀበሉትንም ንፅህና ጠብቀው ቢኖሩ በውስጡ የኃጢአታቸውን ስርየት ያገኛሉ።

ስለዚህም ከክፉ ነገር ሁሉ ተጠብቀን የፈጣሪያችንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የቸርነቱን ብዛት ልናመሰግን ይገባናል እርሱ ስለ እኛ ሰው ሆኖ ከኃጢአታችን አድኖናልና።

ለእርሱም ከቸር አባቱ ሕይወት ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_እንጣልዮስ_ሰማዕት

በዚችም ቀን ከፋርስ አገር ሰዎች ወገን የሆነ የከበረ እንጣልዮስ በሰማእትነት ሞተ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ በሮም አገር የሰራዊት አለቃ መኰንን ሆኖ አስራ አምስት አመት ኖረ።

የክብር ባለቤት ክርስቶስን ንጉስ ዲዮቅልጣኖስ በካደው ጊዜ ይህ ቅዱስ ሰማያዊ መንግስትን መረጠ የዚህ የኃላፊውንም አለም ክብር ንቆ ተወ መጥቶም በከሀዲው ንጉስ ፊት በመቆም እርሱንና የረከሱ አማልክቶቹን ረገመ ንጉሱም ስለ ድፍረቱ ደነገጠ።

ከፋርስ ሰዎችም ከታላላቆቹ ወገን እንደሆነ በአወቀ ጊዜ በሽንገላ በጎ ነገርን ተናገረው ምናልባት ከጌታ ክርስቶስ ሀይማኖት ልቡን መመለስ ቢችል ብሎ ለሰራዊት አለቃ ለኅርማኖስ ሰጠው። ኅርማኖስም ጌታ ክርስቶስን ከማምለክ ሀሳቡን ሊአስለውጠው ባልተቻለው ጊዜ ወደ ንጉሱ መለሰው እርሱም በየራሱ በሆነ ስቃይ አሰቃየው።

ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ ያፀናውና ያረጋጋው ነበር በብዙ በተለያዩ ስቃዮችም እየተሰቃየ ለረጅም ጊዜ ኖረ ብዙ ጊዜም ሰቅለውታልና ከዚያም አርደው ቆዳውን ገፈፉት ምላሱንም ቆረጡት ለነጣቂዎች አውሬዎችም ጣሉት በጨለማ ቤትም ዘጉት ሶስት ጊዜም ነፍሱን አሳለፈ እግዚአብሔርም አስነሳው።

ዲዮቅልጥያኖስም ማሰቃየቱን በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘና ቆረጡት የሰማእትነት አክሊልንም በመንግስተ ሰማያት ተቀበለ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ዮሐንስ_ሊቀ_ዻዻሳት

በዚችም ቀን የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባ ዮሀንስ አረፈ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሰባ አራተኛ ነው። ይህም አባት ሊቀ ጵጵስና ከመሾሙ አስቀድሞ ወደ ህንድ አገር በባሕር ላይ በመርከብ እየሄደ ሁልጊዜ የሚነግድ ነጋዴ ሆኖ ነበር ከዚያ ፊት ግን በምስር ሀገር በሰማዕቱ በቅዱስ መርቆሬዎስ ቤተ ክርስቲያን በፀሀፊነት የሚያገለግል ዲያቆን ነው ፀሀፊነቱንም ትቶ የሚነግድ ሆነ።

በዘጠኝ መቶ አራት አመተ ሰማእታት የካቲት አራት በእሁድ እለት ኤጲስቆጶሳቱ መርጠው ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በመልካም አጠባበቅም መንጋውን የሚጠብቅ ሆነ።ሊቀ ጳጳሳት ሆኖ ከመሾሙ በፊት ሀያ ሽህ ያህል የወርቀወ ዲናር ነበረው ከመሞቱ በፊት ለድኆችና ለችግረኞች ለአብያተ ክርስቲያን ለገዳማትም ሁሉን ገንዘቡን ሰጥቶ ጨረሰ።

በሹመቱም ወራት ከህዝብ ምንም ምን እጅ መንሻ አልተቀበለም በሹመቱም ሀያ ስምንት አመት ኖረ በዘጠኝ መቶ ሰላሳ ሁለት አመተ ሰማእታት በዚች ቀን በጥምቀት በአል አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ወቅሪስ_ገዳማዊ

በዚችም እለት የከበረ ተጋዳይ ለሆነ አባት አባ ወቅሪስ የእረፍቱ መታሰቢያ ነው። ይህም ቅዱስ አባት በባስልዮስ ዘንድ አደገ እርሱም ቅስና ሾመው ይህም ቅዱስ በደም ግባቱ በላህዩ ደስ የሚል ፊቱም የሚያምር ነበር።

በቀድሞው ግብሩ ወጣት ሆኖ ሳለ የሹሙን ሚስት ተመኛትና እጅግም ወደዳት እርሷም ወደደችው ወደ ሌላ ቦታ ሄደው ፍላጎታቸውን ይፈፅሙ ዘንድ ተማከሩ ለዚህም ነገር ሲዘጋጁ በህልሙ ራእይን አየ። እርሱ ታስሮ በፍርድ አደባባይ ቆሞ ነበር ሌሎችም ብዙዎች እስረኞች ከእርሱ ጋር አሉ ስለ በደላቸውም እያንዳንዳቸውን ይመረምሯቸው ነበር እርሱም በልቡ የታሰርኩት በምን ይሆን ባሏን ልነጥቀው ስለፈለግሁ ስለዚያች ሴት ነውን እርሱ ከስሶኝ ወደዚህ ታላቅ ግዳጅ ላይ አደረሰኝን አለ።

በዚህም ነገር እየተሸበረ ሳለ በቀድሞ ወዳጁ አምሳል አንድ ሰው መጣና የታሰርከው በምንድን ነው? አለው ስለ ሀጢያቱ ስለ አፈረ ሊሰውረው ወደደ ግድ ባለውም ጊዜ እንዲህ ነገረው ወዳጄ ሆይ እገሌ ስለሚስቱ የከሰሰኝ ይመስለኛል ስለዚህም ፈርቼ እሸበራለሁ በወዳጁ አምሳል ወደርሱ የመጣው መልአክም ወዳጄ ሆይ ይህን ስራ እንዳትሰራ ወደርሱም እንዳትመለስ በቅዱስ ወንጌል ማልልኝ እኔም ዋስ እሆንሀለሁ አለው በወንጌልም ማለለት በዚያንም ጊዜ ከእንቅልፉ ነቃ ያየው ራእይም እውነት እንደሆነ አወቀ።

ስለዚህም አገሩን ትቶ ወደ እስክንድርያ ሄደ በዚያም ስሟ ኄራኒ የሚባል እግዚአብሄርን የምትፈራ አንዲት ሴት አገኘ በተነጋገሩም ጊዜ የልቡን ሁሉ ነገራት እርሷም እነዚህን ያማሩ ልብሶችህን ተው ተርታ ልብስንም ለብሰህ እግዚአብሄርን አገልግለው አለችው።ከዚያም ወደ በርሀ ሄደ ከብዙ ተጋድሎ የተነሳ ሆዱ እንደ ድንጋይ እስከ ደረቀ ድረስ ቅጠላቅጠል እየበላ ኖረ ጌታችንም ወደርሱ መጥቶ ፈወሰው።

አጋንንትም ስለሚፈታተኑትና ስለሚያሰቃዩት እርሱ በፆምና በፀሎት በመጋደል በክረምት ዝናብ እየወረደበት ራቁቱን ቆሞ ያድራል በበጋም በቀን የፀሀይ ትኩሳት በሌሊትም ቁር ሰማያዊ ሀብት እስከተሰጠው ድረስ መላእክትም ወደርሱ መጥተው ሰማያዊ ኅብስትን ሰማያዊ መጠጥን ይመግቡት ነበር።

የተሰወሩ ራእዮችን ያውቅ ዘንድ ተገባው ሶስት ድርሰቶችንም ደረሰ አንዱ በበረሀ ስለሚኖሩ ሁለተኛው በአንድነት ስለሚኖር መነኮሳት ሶስትኛው ስለካህናት ነው።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

12 Jan, 11:30


የኦርቶዶክስ ተዋህዶ የጥምቀት መዝሙር ይፈልጋሉ?

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

10 Jan, 19:22


#ጥር_3

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሦስት በዚች ቀን
#የቤተልሔም_ሕፃናት በኄሮድስ ተገደሉ፣ የከበረ አባት #የአባ_ሊባኖስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ኄሮድስ_ያስገደላቸው_ሕፃናት

ጥር ሦስት በዚች ቀን ኄሮድስ ከሰብአ ሰገል እንደ ተረዳው ዘመን ልክ ሁለት ዓመት የሆናቸው ከዚያም በታች የሆኑ በቤተ ልሔምና በአውራጃዋ ሁሉ ያሉ ሕፃናት ተገደሉ። ቊጥራቸውም ዐሥራ አራት እልፍ ከአራት ሺህ ነው እነርሱም ከሴቶች እንደ ተወለዱ ንጹሐን የሆኑ ናቸው።

በከበረ ወንጌል እንደተነገረ ሰብአ ሰገልም ከሔዱ በኋላ እነሆ ኄሮድስ ሕፃኑን ሊገድለው ይሻዋልና ተነሣ ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ ግብጽ ሽሽ ተመለስ ብዬ እስከምነግርህም ከዚያ ኑር ብሎ የእግዚአብሔር መልአክ ለዮሴፍ በሕልም ነገረው። እርሱም በሌሊት ተነሥቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ግብጽ ሔደ ኄሮድስ እስቲሞት ድረስም በዚያ ኖረ ከእግዚአብሔር ዘንድ ልጄን ከግብጽ ጠራሁት ተብሎ በነቢይ የተነገረው ይፈጸም ዘንድ።

ከእነዚህ ውስጥ የክብር ባለቤት ጌታችን ክርስቶስ አንዱ እንደሚሆን ኄሮድስ አስቧልና። ጌታችንም ሥራውን ሁሉ ከብቻዋ ከኃጢአት በቀር ሠራ በረቀቀ ጥበቡም ከኄሮድስ ፊት ሸሸ ኄሮድስ አግኝቶት ሊገድለው ቢአስብ ያለ ጊዜው መግደል ባለተቻለውም ነበርና ሰነፎች ሰዎች ሰው መሆኑን ምትሐት ነው ብለው በአሰቡ ነበር ስለዚህ የክብር ባለቤት ጌታችን ሸሸ ሁለተኛም እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተቀምጦ ወደ ግብጽ ይወርዳል ተብሎ የተነገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ዳግመኛም ከክፉ ነገር እንድንሸሽ ለእኛ ሊአስተምረን የግብጽንም ጣዖታት ያጠፋቸው ዘንድ ነው።

ይህን ያህል ብዛት ያላቸውን ሕፃናት መሰብሰብና መግደል ለኄሮድስ እንዴት ተቻለው ተንኰለኛ ኄሮድስ ምክንያት ፈጥሮ የሁለት ዓመትና ከዚያም ያነሱ ሕፃናትን አሳድገን ጭፍራ እንሠራለት ዘንድ የሚያዝ የንጉሠ ነገሥት ቄሣር ደብዳቤ ከእኔ ዘንድ ደርሷል ወርቅ ብር ቀለብ ልብስም እንሰጣለን ብሎ ወደ ሀገሩ ሁሉ ላከ። ስለዚህም ከእናቶቻቸው ጋር ተሰበሰቡ ያን ጊዜ ከእርሱ ዘንድ አንድ ሽህ ሁለት መቶ ወታደሮችን አውጥቶ በተራራ ላይ አረዱአቸው። ነቢይ ኤርምያስም የተናገረው ተፈጸመ ራኄል ስለ ልጆቿ ስታለቅስ ብዙ መከራ ጩኸት ሙሾ ልቅሶ ዋይታ በራማ ተሰማ ልቅሶ መተውን መጽናናትን እምቢ አለች ልጆቿ ልጆችን አልሆኗትምና።

ዮሐንስም በራእዩ እንዲህ አለ በታላቅ ቃል ጮኹ የተመሰገንህ እውነተኛ አቤቱ እስከ መቼ ነው ስለ ደማችን ተበቅለህ በምድር ላይ በሚኖሩ ሰዎች አትፈርድባቸውምን አሉ። ከእነርሱም ወገን ለየአንዳዱ ብሩህ ልብስ ሰጥተው እንግዲህ ጥቂት ቀን ዕረፉ አሉዋቸው። እንደነርሱ ላሉ ለእግዚአብሔር ባለሟሎች እንደነርሱ ይሞቱ ዘንድ ያላቸው ወንድሞቻቸው እስከሚፈጸሙበት ቀን ድረስ እንዲህ የእሊህን ሕፃናት ነፍሳቸውን አይቷልና።

ዳግመኛም እንዲህ አለ በዙፋኑ ፊት በአራቱ እንስሶችና በሃያ አራቱ አለቆች ፊት አዲስ ምስጋና ያመሰግናሉ ከግብጽ ምድር ከተዋጁ ከዐሥራ አራት እልፍ አራት ሽህ ሕፃናት በቀር ያቺን ምስጋና ሊያውቃት የሚቻለው የለም። እነርሱም ከሴቶች እንደ ተወለዱ ንጹሐን የሆኑ ናቸው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ሊባኖስ_ዘመጣዕ

በዚህችም ዕለት ዳግመኛ የከበረ አባት የአባ ሊባኖስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው ይኸውም መጣዕ ነው። የዚህ ቅዱስ የአባቱ ስም አብርሃም የእናቱም ስም ንግሥት ነው እነርሱም በወርቅና በብር እጅግ የበለጸጉ ሮማዊ ናቸው:: ልጃቸውን አባ ሊባኖስን በሃይማኖት በምግባር ኮትኩተው ካሳደጓቸው በኋላ ዕድሜያቸው ሲደርስ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ያጋቧቸው ዘንድ ከቁስጥንጥንያ አገር ሚስት ባመጡለት ጊዜ እርሱ ግን ፈጽሞ እምቢ አለ፡፡ ወደጫጉላቤትም መግባትን እምቢ አለ፡፡ በዚህም ጊዜ ነቢዩ ሳሙኤልን እንደጠራው አባታችንንም እግዚአብሔር ሦስት ጊዜ በስማቸው ጠራቸውና ‹‹ከአባትህ ተለይ አንተ የመንግሥተ ሰማያት ሙሽራ ነህ እንጂ የዚህ ምድራዊ ዓለም ሙሽራ አይደለህም›› አላቸው፡፡ አባታችንም ‹‹ወዴት እሄዳለሁ? ምንስ ላድርግ?›› ባሉ ጊዜ ወዲያው የታዘዘ መልአክ በሌሊት መጥቶ ከአባታቸው ቤት አውጥቶ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስ ዘንድ አደረሳቸው፡፡ ታላቁ አባት አባ ጳኩሚስም ለአባ ሊባኖስ በዓት በመስጠት ገዳመ ሥርዓትን፣ አስኬማ መላእክትን፣ ቅናተ ዮሐንስን አስተምረዋቸው አመነኮሷቸውና ከ8ቱ ቅዱሳን ጋር እንዲገናኙ አደረጓቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ያ ከአባታቸው ቤት ወስዶ አባ ጳኩሚስ ገዳም ያደረሳቸው ያ መልአክ ድጋሚ ተገለጠላቸውና ‹‹ወደ ቅድስት ሀገር ኢትዮጵያ ሂድና ተጋድለህን በዚያ ፈጽም ዝናህ በስፋት ይነገራል፣ ለብዙዎችም አባት ትሆናቸዋለህ›› አላቸው፡፡ ቀጥሎም ራሱ መልአኩ ወደ ኢትዮጵያ አመጣቸውና በአክሱም ተቀመጡ፡፡ በዚያም ብዙ ከተጋደሉ በኋላ ወደ ሸዋ መጡና ወንጌልን ዞረው አስተምረው ብዙ ድውያንን ፈውሰው ከዓመታት ቆይታ በኋላ ተመልሰው አክሱም ሄዱ፡፡ በአክሱምም 7 የተለያዩ ጸበሎችን ከድንጋይ ላይ በተአምራት አፍልቀው ድውያንን ፈውሰው ዕውራንን አበሩ፡፡ በዓታቸውንም ከአክሱም ጽዮን ፊት ለፊት አድርገው ሲኖሩ ከዕለታት በአንደኛው ቀን አባታችን በተአምራት ከጭንጫ ካፈለቁት ጸበል ‹‹ተራ ውሃ ነው›› ብላ አንዲት ሴት ልጇን አዝላ ልትቀዳ መጣች፡፡ ወዲውም ከቦታው ስትደርስ አድጧት ወደቀችና ልጇም አምልጥጧት ልቡን ድንጋይ መቶት ሞተ፡፡ ሴትዮዋም ስትጮህ አባ ሊባኖስ ፈጥነው ወጡና በልጁ ላይ ጸልየው በመስቀል ምልክት አማትበው ከሞት አስነሥተውታል፡፡ ሕፃኑ ልጅ ከሞት እንደተነሣ ‹‹አምላከ አባ ሊባኖስ›› ብሎ አመሰገነ፡፡

ይህንንም ደግ ሥራቸውንና ተአምራታቸውን ያዩ አንዳንድ እኩይ ካህናት በቅናት ተመልተው ‹‹ምትሃት ነው የሚያሳየው›› ብለው በጻድቁ ላይ ሕዝቡን አሳደሙባቸው፡፡ አባታችንም ካህናቱን ለመምከር ቢሞክሩም አላስቀምጥ አሏቸው፡፡ ይልቁንም ጦር ጦራቸውን ይዘው አሳደዷቸው፡፡ አባታችንም በዚህ እጅግ አዝነው ከአክሱም ተነሥተው ደርቃ ወደምትባል ቦታ ሄዱ፡፡ በዚያም በጾም በጸሎት እየተጋደሉ ሲኖሩ በእነዚያ በጠሏቸውና በክፋት በተነሡባቸው ካህናት አገር ግን ለ3 ዓመት ምንም ዝናብ ሳይዘንብ ቀረ፡፡ አባታችን በተሰደዱባት በደርቃ አገር ግን ብዙ ዝናብ ይዘንብ ነበር፡፡ አባታችን በዚያችም አገር እንደልማዳቸው ከዐለት ላይ ውኃ አፍልቀው በውኃው ብዙ ድውያንን ፈውሰውበታል፡፡ በዚያም ትልቅ በዓት መሥርተው በተጋድሎ ሲኖሩ በክፉ የተነሡባቸው እኩይ የሆኑ ካህናት መጥተው ‹‹አባታችን በከንቱ አምተንሃል በድለንሃልና ይቅር በለን፣ በድርቅ ማለቃችን ነውና ዝናብም እንዲዘንብልን ጸልይን›› ብለው ከእግራቸው ሥር ወደቁ፡፡ አባታችንም ይቅር ብለው ከፈጣሪ አማለዷቸው፡፡ ዝናቡም ወዲያው ዘነበላቸውና በአገሪቱ ጥጋብ ሆነ፡፡

ከዚህም በኋላ አባታችን አስቀድመው ወዳዩአት ወደ ሸዋ ምድር ግራርያ መጡና በዓታቸውን በአሰቦት ጫካ አደረጉ፡፡ ነገር ግን መልአኩ ተገልጦላቸው ‹‹ሊባኖስ ሆይ! ከዚህ ቦታ የአንተ መኖሪያ አይደለም፣ በዚህ ቦታ ላይ እግዚአብሔርንና ሰውን የሚያገናኝ የሚያስታርቅ ታላቅ ጻድቅ ይወጣበታልና ይህ ቦታ የእርሱ ርስት ነው፣ የብዙ መነኮሳትም መንደር ይሆናል ነገር ግን የቦታው ስም በአንተ ስም ይጠራልሃል›› አላቸው፡፡ በኋላ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ተወልደው በዓታቸውን በዚያ ቦታ ላይ ሲያጸኑ ቦታው ግን ‹‹ደብረ ሊባኖስ›› ተብሎ በመጀመሪያው አባት ስም ተሰየመ፡፡ መልአኩም በሌሊት እየመራ ወደ አክሱም

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

09 Jan, 20:42


✝️ #ጥር_2 ✝️


✝️ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ሁለት በዚች ቀን ደሙ በግፍ የፈሰሰ
#ጻድቁ_አቤል አረፈ፣ የከበረ አባት #ቅዱስ_አላኒቆስ ኤጲስቆጶስ በሰማዕትነት ሞተ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #ቅዱስ_ቴዎናስ አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አቤል_ጻድቅ

ጥር ሁለት በዚች ቀን ደሙ በግፍ የፈሰሰ ጻድቁ አቤል አረፈ እርሱም ወንድሙ ቃየል የገደለው የሙታን በኵር የሆነ ነው።

ምክንያቱም አዳም የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ተላልፎ እንዳይበላው የታዘዘውን ዕፅ በላ ያን ጊዜ በእርሱና በልጆቹ ላይ ሞት ሠለጠነ ለኃጢአትም ተገዥ ሆነ። ሰይጣንም ሰውን ለማሳት ሠለጠነ ከዚህም በኋላ አዳም ከገነት ወጥቶ ወደታችኛዋ ምድር ወረደ ስለ በደሉና የፈጣሪውንም ትእዛዝ በመተላለፉ ፈጽሞ እያዘነና እያለቀሰ መቶ ዓመት ኖረ።

ከዚህም በኋላ አዳም ሔዋንን በግብር አወቃት ፀንሳ ቃየልንና እኅቱን ኤልዩድን ወለደች ሁለተኛም ዐወቃት አቤልንና እኅቱን አቅሌማን ወለደቻቸው አዳምም ሔዋንን እነሆ ልጆችሽ አካለ መጠን አደረሱ ጐለመሱ ቃየል የአቤልን እኅት አቅሌማን ያግባት አቤልም የቃየልን እኅት ኤልዩድን ያግባት አለ።

ቃየልም እናቱን ሔዋንን እንዲህ አላት ለእኔ ከእኔ ጋር የተወለደች እኅቴን ማግባት ይገባኛል አቤልም ከእርሱ ጋር የተወለደች እኅቱን ያግባ ቃየል ከእርሷ ጋር የተወለደ ኤልዮድም እናቷ ሔዋንን የምትመስል እጅግ የምታምር መልከ መልካም ናትና።

አዳምም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ ጭንቅ ሆነበት ቃየልንም አብራህ የተወለደች እኅትህን ታገባት ዘንድ አይገባህም አለዚያም ለእግዚአብሔር መሥዋዕትን አቅርቡና መሥዋዕቱን ለተቀበለው ይሁን አለው።

መሥዋዕትንም በአቀረቡ ጊዜ የአቤልን መሥዋዕት እግዚአብሔር ተቀበለ የቃየልን ግን አልተቀበለም ስለዚህም ቃየል ፈጽሞ አዘነ ሰይጣንም ተገናኘውና ምን ያሳዝንሃል አለው ቃየልም ለወንድሜ ለአቤል እኅቴን እተውለት ዘንድ አባቴ አዘዘኝ አለው። ሰይጣንም ምክርን ከኔ ስማ ወንድምህን ወደ ውኃ ምንጭ ይዘኸው ሒድ ውኃንም ሲጣጣ ራሱን በደንጊያ ምታው በሞተ ጊዜ ሁለቱንም ታገባቸዋለህ የሚከለክልህ ማነው አለው ለቃየልም የሰይጣን ምክር ደስ አሰኘው ልቡም በዝሙት እሳትነት ነደደ ሰይጣን እንዳስተማረውም ወንድሙን አቤልን ገደለው ለሴት ስለ መቅናትም ጻድቁ አቤል በወንድሙ እጅ ሞተ እንዲህም ሞት ወደ ዓለም ገባ።

እግዚአብሔርም ቃየልን ወንድምህ አቤል ወዴት ነው አለው። ቃየልም አላውቅም በውኑ እኔ የአቤል ጠባቂው ነኝን አለው። እግዚአብሔርም እንዲህ አለው ቃየል ምን አድርገሃል የወንድምህ የአቤል ደም ጩኸት ከምድር ወደኔ ደርሷል። አሁንም በእጅህ የፈሰሰውን የወንድምህን ደም ትጠጣ ዘንድ አፍዋን የከፈተች ምድር የተረገመች ትሁን አንተ ታርሳታለህና በረከቷን ትሰጥህ ዘንድ አትጨምርም በምድር ላይ ፈሪ ተቅበዝባዥ ሁን።

ይህም መርገም ዘሩ በጥፋት ውኃ ከምድር ገጽ እስከ ሚደመሰስ በቃየል ላይ የበዛ ሆነ። የክብር ባለቤት ጌታችንም ጸሐፍት ፈሪሳውያንን ሲዘልፋቸው እንዲህ አላቸው ስለዚህ ነቢያትን ሊቃውንትን ጥበበኞችን ወደናንተ እልካለሁ ከነርሱ የምትገድሉት አለ የምትሰቅሉትም አለ በምኵራባችሁ የምትገርፉት አለ ካንድ አገር ወዳንድ አገር ታሳድዷቸዋላችሁ።

ከጻድቁ ከአቤል ጀምሮ በቤተ መቅደስና በመሠዊያው መካከል እስከገደላችሁት እስከ በራክዩ ልጅ እስከ ዘካርያስ ደም ድረስ በዓለም የፈሰሰው የጻድቃን ደም ሁሉ በእናንተ ላይ ይደርስ ዘንድ።

ጳውሎስም አለ ቃየል ካቀረበው መሥዋዕት ይልቅ አቤል በሃይማኖት ለእግዚአብሔር ያቀረበው መሥዋዕት ተሻለ ስለ እርሱም ደግ እንደሆነ መሰከረለት መሥዋዕቱንም በመቀበሉ ምስክሩ እግዚአብሔር ነው ደግ እንደሆነም ከሞተ በኋላ ተናገረ።

ከዚህም በኋላ አዳም ልጁን በአጣው ጊዜ ወንድምህ አቤል ወዴት አለ ብሎ ቃየልን ጠየቀው ቃየልም በቁጣ አላውቅም እኔ የአቤል ጠባቂው ነውኝን ብሎ መለሰ አዳምም ልጁን ይፈልግ ዘንድ ወደ ዱር ሮጠ በወንዝ ዳርም በድኑን አገኘና አንገቱን አቅፎ ማን ገደለህ አለው ከበድኑም ወንድሜ ቃየል ገደለኝ የሚል ቃል ወጣ። አዳምና ሔዋንም በልጃቸው በአቤል ሞት ሃያ ስምንት ዓመት ያህል ሲያለቅሱ ኖሩ።

ከዚህም በኋላ መላእክት ወደ አዳም መጥተው የዓለሙ ሁሉ አባቶች አባት አዳም የምሥራች እነሆ ልጅህ አቤል የገነትን ዛፎች ተሳለመ ነፍሱም እንደ ተወደደ መሥዋዕት ወደ እግዚአብሔር ዐረገች አሉት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አላኒቆስ_ሰማዕት

በዚህችም ቀን የከበረ አባት አላኒቆስ ኤጲስቆጶስ በሰማዕትነት ሞተ። እርሱ ጣዖታቱን እንዲአቃልሉ ለሰዎች እንደሚያስተምራቸው ከሀዲው ንጉሥ በሰማ ጊዜ ይዘው ጽኑ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ መልእክተኞችን ላከ።

የንጉሥ መልክተኞች መላካቸውን የተመሰገነ አላኒቆስ ሰምቶ በሀገረ ስበከቱ ያሉትን ሕዝቦች ሰበሰባቸውና የቁርባን ቅዳሴን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው። ከዚህም በኋላ በቀናች ሃይማኖት ጽኑ ከእንግዲህ ፊቴን አታዩኝም አላቸው። እነርሱም አለቀሱ ሊአስተዉትም አልተቻላቸውም ወጥቶም ራሱን ለንጉሥ መልክተኞች አሳልፎ ሰጠ እነርሱም ወስደው ለእንዴናው አገር መኰንን ሰጡት። እርሱም ወደ ሀገረ እንድኩ ወስዶ በዚያ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ማሠቃየቱም በሰለቸው ጊዜ ትከሻውን በሰይፍ ይሠነጥቁ ዘንድ ራሱንም ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ መሞቱን አውቆ አማንያን ከሆኑ መርከበኞች አንዱን እንዲህ ብሎ አዘዘው ወደ ወደቡ ስትደርሱ ሥጋዬን በኮረብታ ላይ አድርግ እርሱም እንዳዘዘው አደረገ።

ከዚህም በኋላ ምእመናን ሰዎች መጥተው ሥጋውን ወስደው ገነዙት የስደቱም ወራት እስቲያልፍ በእነርሱ ዘንድ አኖሩት ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው ሥጋውን በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶች ተደረጉ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባት_ቴዎናስ_ሊቀ_ጳጳሳት

በዚህችም ዕለት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት ቴዎናስ አረፈ። እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ዐሥራ ስድስተኛ ነው። ይህም ቅዱስ አዋቂ ብልህ በቀናች ሃይማኖትም የጸና በሥራው ሁሉ ያማረ ስለ ዕውቀቱም ሰዎች ሁሉ የሚወዱትና የሚሹት ሆነ።

በዚያም ወራት ከሀዲያንን በመፍራት በሥውር ከዋሻ ውስጥ በቀር በግልጥ ሊጸልዩና ሊቀድሱ ለክርስቲያኖች አልተቻላቸውም ነበር ይህም አባት አብያተ ክርስቲያናትን እስከሠሩ ድረስ አግባባቸው በእመቤታችንም በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠሩ ከከሀዲያንም ብዙዎችን መልሶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃችው።

በተሾመባት በመጀመሪያ ዓመት ተፍጻሜተ ሰማዕት የሆነ ሊቀ ጳጳሳት ጴጥሮስን ያጠመቀው እርሱ ነው። በተሾመ በአምስተኛ ዓመቱም አናጒንስጢስነት ሾመው በዐሥራ ሁለተኛም የሹመቱ ዓመት ቅስና ሾመው።

በዚህም አባት ዘመን አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ አንድ ገጽ ነው የሚል ከሀዲ ሰባልዮስ በእስክንድርያ አገር ተነሣ ይህም አባት አውግዞ ለየው የከፋች ሃይማኖቱንም አጠፋት። ዳግመኛም በዘመኑ ቆዝሞስና ድምያኖስ ወንድሞቻቸው እናታቸው ቴዎዳዳም በሰማዕትነት ሞቱ ይህም አባት ያማረ ጒዞውን በመጓዝ እግዚአብሔርን አገልግሎ በሰላም አረፈ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥር)

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

08 Jan, 19:10


✝️ #ጥር_1✝️


✝️ አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥር አንድ ቀን የዲያቆናት አለቃ የሰማዕታት መጀመሪያ የሆነ የከበረ
#ቅዱስ_እስጢፋኖስ ምስክር ሆኖ ሞተ፣ #ቅዱስ_ለውንድዮስ በሰማዕትነት ሞተ፣ የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #አባ_መቃርስ አረፈ፣ #ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስ_እና_ሰከላብዮስ (#ቅዱሳን_ሰማዕታተ_አክሚም) በሰማዕትነት አረፉ፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_እስጢፋኖስ_ቀዳሜ_ሰማዕት

በዚህችም ጥር አንድ ቀን የዲያቆናት አለቃ የሰማዕታት መጀመሪያ የሆነ የከበረ እስጢፋኖስ ምስክር ሆኖ ሞተ። ለዚህም ለከበረ እስጢፋኖስ የእግዚአብሔርን ኃይልና ጸጋ የተመላ ሰው እንደነበረና በሕዝቡም መካከል ታላላቅ ተአምራትንና ድንቅ ሥራን ይሠራ እንደነበረ የሐዋርያት ሥራ የተባለ መጽሐፍ ስለርሱ ምስክር ሆነ።

ከዚህም በኋላ አይሁድ ቀኑበት የሐሰት ምስክሮች የሚሆኑ ሰዎችንም አስነሡበት ይህን ሰው በሙሴና በእግዚአብሔር ላይ የስድብ ቃልን ሲናገር ሰምተነዋል እንዲሉ ሐሰትን አስተማሩአቸው። ሕዝቡንና ሽማግሌዎችን ጸሐፊዎችንም አነሣሡአቸው አዳርሱን ብለው ከበው እየጐተቱ ወደ ሸንጎ ወሰዱት።

የሐሰት ምስክሮችንም አቆሙበት እነርሱም ይህ ሰው በቤተ መቅደስ ላይ በኦሪትም ላይ ስድብን ሲናገር ተው ብንለው እምቢ አለ። የናዝሬቱ ኢየሱስ ቤተ መቅደሳችሁን ያፈርሰዋል ሙሴ የሰጣችሁን ኦሪታችሁንም ይሽራል ሲል ሰምተነዋል አሉ።

በአደባባይ ተቀምጠው የነበሩት ሁሉ ተመለከቱት ፊቱንም የእግዚአብሔርን መልአክ ፊት ሁኖ አዩት። ሊቀ ካህናቱም እውነት ነውን እንዲህ አልክ አለው። እርሱም እንዲህ አለ ወንድሞቻችንና አባቶቻችን ስሙ ወደ ካራን ከመምጣቱ አስቀድሞ በሶርያ ወንዞች መካከል ሳለ ለአባታችን ለአብርሃም የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ተገለጠለት። ካገርህ ውጣ ከዘመዶችህም ተለይ እኔ ወደማሳይህ ሀገርም ና አለው።

ከዚህም በኋላ ከከላውዴዎን ወጥቶ በካራን ተቀመጠ አባቱም ከሞተ በኋላ ዛሬ እናንተ ወደ አላችሁባት ወደዚች አገር አመጣው። ከዚህም በኋላ የግዝረትን ሥርዓት ሰጠው ይስሐቅንም በወለደው ጊዜ በስምንተኛው ቀን ገዘረው እንዲሁ ይስሐቅም ያዕቆብን ገዘረው ያዕቆብም ዐሥራ ሁለቱን ነገድ አባቶችን ገዘረ።

የቀደሙ አባቶቻችንም በዮሴፍ ላይ ቀንተው ወደ ግብጽ አገር ሸጡት እግዚአብሔር ግን አብሮት ነበር። ከመከራው ሁሉ አዳነው በግብጽ ንጉሥ በፈርዖን ፊትም ዕውቀትን መወደድን ሰጠው በግብጽ አገር ሁሉና በቤቱ ሁሉ ላይ ሾመው። ነገርም በማስረዘም በሰሎሞን እጅ እስከተሠራችው ቤተ መቅደስ ያለውን ተረከላቸው።

ከዚህም በኋላ ድምፁን ከፍ ከፍ አድርጎ እናንተም እንደአባቶቻችሁ ዘወትር መንፈስ ቅዱስን የምታሳዝኑት ዐይነ ልቡናችሁ የታወረ ዕዝነ ልቡናችሁ የደነቈረ አንገተ ደንዳኖች አላቸው። አባቶቻችሁ ከነቢያት ያላሳደዱት ያልገደሉት ማን አለ እናንተ ክዳችሁ የገደላችሁትን የአምላክን መምጣት አስቀድመው የነገሩዋችሁን ገደላችኋቸው።

በመላእክት ሥርዓት ኦሪትን ተቀብላችሁ አልጠበቃችሁም። ይህንንም ሰምተው ተበሳጩ ልባቸውም ተናደደ ተነሣሣ ጥርሳቸውንም አፋጩበት። በእስጢፋኖስም መንፈስ ቅዱስ አደረበት ሰማይም ተከፍቶ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ የእግዚአብሔርን ክብር አየ። እነሆ ሰማይ ተከፍቶ የሰው ልጅም በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ አያለሁ አለ።

ጆሮአቸውን ይዘው በታላቅ ድምፅ ጮኹ በአንድነትም ከበው ጐተቱት። እየጐተቱም ከከተማ ወደ ውጭ አውጥተው በደንጊያ ወግረው ገደሉት የገደሉትም ሰዎች ልብሳቸውን ሳውል ለሚባል ጐልማሳ ልጅ ያስጠብቁ ነበር። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ነፍሴን ተቀበል እያለ ሲጸልይ እስጢፋኖስን በደንጊያ ወገሩት።

ዘለፍለፍ ባለ ጊዜም ድምፁን ከፍ አድርጎ አቤቱ ይህን ኃጢአታቸውን ይቅር በላቸው በደልም አታድርግባቸው ይህንንም ብሎ አረፈ። ደጋግ ሰዎችም መጥተው የእስጢፋኖስን ሥጋ ወስደው ቀበሩት ታላቅ ልቅሶም አለቀሱለት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ለውንድዮስ_ሰማዕት

በዚችም ዕለት በከሀዲው መክስምያኖስ ዘመነ መንግሥት ከሶርያ አገር የከበረ ለውንድዮስ በሰማዕትነት ሞተ። የዚህንም ቅዱስ ዜና እግዚአብሔርን የሚያመልክ ተጋዳይ እንደሆነ ንጉሥ መክስምያኖስ በሰማ ጊዜ ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሃይማኖቱንም ትቶ አማልክቶቹን ያመልክለት ዘንድ ብዙ ገንዘብ አቀረበለትና ይሸነግለው ጀመረ የከበረ ለውንድዮስ ግን ዘበተበት ስጦታውንም በማቃለል ክብሩን አጐሳቈለ የረከሱ አማልክቶቹንም ረገመ።

ያን ጊዜ እጅግ ተቆጥቶ በመንኰራኲር ውስጥ ሰቅለው ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን እንዲአሠቃዩት አዘዘ። ንጉሥ እንዳዘዘ አደረጉበት የክብር ባለቤት ጌታችን ግን ያለ ጥፋት በጤና አወጣው።

ዳግመኛም በብረት ዘንጎች ይደበድቡት ዘንድ ቅባትና ስብንም በታላቅ ድስት አፍልተው ቅዱስ ለውንድዮስን ከውስጡ ይጨምሩት ዘንድ አዘዘ ይህን ሁሉ ሥቃይንም አሠቃዩት የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያጸናውና ያስታግሠው ያለ ጉዳትም በጤና ያስነሣው ነበር።

ማሠቃየቱንም በደከመው ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ከሥጋውም ድንቆች የሆኑ ብዙዎች ተአምራቶች ተገለጹ ዜናውም በሶርያ አገር ሁሉ ተሰማ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማት ተሠሩለት ከገዳማቱም በአንዲቱ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት የሆነው የከበረ ሳዊሮስ በሕፃንነቱ ተጠመቀባት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_መቃርስ_ሊቀ_ዻዻሳት

በዚህችም ቀን የእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አባ መቃርስ አረፈ፡፡ እርሱም ለአባቶች ሊቃነጳጳሳት ስልሳ ዘጠነኛ ነው። ከእርሱ በፊት የነበረ አባ ሚካኤልም በአረፈ ጊዜ ኤጲስቆጶሳትና ሊቃውንቱ የግብጽም ታላላቆች ሁሉም ወደ አስቄጥስ ገዳም ወጥተው ለዚች ለከበረች ሹመት ስለሚገባ ከዋሻ ውስጥ ከሚኖሩ ደጋጎች ገዳማውያን ሲጠያየቁና ሲመረምሩ ኖሩ። ከዚህም በኋላ አንድ ጻድቅ ሰው ስለዚህ አባት ነገራቸው እንዲህም አላቸው በአባ መቃርስ ገዳም የሚኖር ቀሲስ አባ መቃርስ እርሱ ለዚች ሹመት ይገባል።

በዚያንም ጊዜ ፈልገው ያዙት እርሱም እኔ ለዚች ሥራ የማልጠቅም በደለኛ ነኝ እያለ ሲጮህ ያለ ፈቃዱ አሥረው ወሰዱት ሊቀ ጵጵስና ሾሙት እንጂ እርሱ የሚላቸውን ቃሉን አልሰሙትም።

ከዚህም በኋላ የሊቀ ጵጵስናውን ሥራ መሥራት ጀመረ በግብጽ አገር በሁሉ ቦታ ኤጲስቆጶሳትን ካህናትን ሾመ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትንም አደሰ ጊዜውም ያለ ኀዘን የጤንነትና የሰላም ጊዜ ነበር። ሹመቱም ሃያ ሰባት ዓመት ከአርባ አንድ ቀን ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱሳን_ዲዮስቆሮስ_እና_ሰከላብዮስ (#ቅዱሳን_ሰማዕታተ_አክሚም)

በዚህችም ዕለት የከበሩ የአክሚም ሰማዕታት የምስክርነታቸውን ተጋድሎ ፈጸሙ ዜናቸውም እንዲህ ነው። አክሚም በሚባል አገር ሹም የሆነ አንድ ሰው ነበረ በወርቅ በብር ባለጸጋ ነው ስሙም አልሲድማልዮስ ይባላል ስማቸው ዲዮስቆሮስና ሰከላብዮስ የሚባል ሁለት ልጆችን ወለደ እነርሱም ከመጾምና ከመጸለይ ጋር እግዚአብሔርን በመፍራት አደጉ።

አባታቸውም በሞተ ጊዜ ምንኲስናን ተመኙ የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦላቸው ወደ ገዳማዊ አባ ሙሴ ገዳም እንዲሔዱ አዘዛቸው ሒደውም በዚያ መነኰሱ ድንቆች ተአምራቶችንም እያደረጉ በብዙ ተጋድሎ ኖሩ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

07 Jan, 20:43


#ታኅሣሥ_30

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሠላሳ በዚች ቀን በአባ መቃርስ ገዳም በአስቄጥስ አበ ምኔት የሆነ የከበረ አባት
#አባ_ዮሐንስ አረፈ፣ የትንቢትና በሽተኞችን የመፈወስ ሀብት ተሰጠው የተመሰገነ #የአባ_ዮሐንስ_ብጹዕ አረፈ፣ #ቅዱሳን_ኮርዮንና_ፊልሞና ከእነርሱም ጋር አርባ ወታደሮች በሰማዕትነት ሞቱ፣ ተጋዳይ የሆነ #አባ_ዘካርያስ_ገዳማዊ አረፈ፡፡



#አባ_ዮሐንስ_አበ_ምኔት

ታኅሣሥ ሠላሳ በዚህች ቀን በአባ መቃርስ ገዳም በአስቄጥስ አበ ምኔት የሆነ የከበረ አባት አባ ዮሐንስ አረፈ።

ይህም አባት በተሾመ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን በራች ለብዙ ቅዱሳንም አባት ሆነ ከእርሳቸውም ውስጥ ታላላቅ ከዋክብት የሆኑ አባ ገዐርጊና አባ አብርሃም የሀገረ ተሙዝ ኤጲስቆጶስ አባ ሚናስ የሀገረ ስሐ አባ ዘካርያስ ለብዙ ሰዎች ነፍሳት ወደብ የሆኑ እነርሱን የመሰሉ ሌሎች ብዙዎች አሉ። ለሕዝቡ ቅዱስ ቊርባንን በሚያቈርብ ጊዜ ኃጢአተኛውና ጻድቁ ይገለጥለታል ከቅዱሳን መላእክቶቹ ጋር ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንም በመሠዊያው ላይ ብዙ ጊዜ አየው።

በአንዲትም ዕለት ሥራው የከፋ አንዱን ቄስ ወደ ቤተክርስቲያን ሲመጣ አየው ከእርሱም ጋር ያሉ ብዙዎች ርኩሳን የረቀቁ አጋንንት ከበውት አፉ ውስጥ ልጓም አድርገዋል ወደ ቤተ ክርስቲያንም ከመግባቱ በፊት የእግዚአብሔር መልአክ ከመሠዊያው ወጥቶ በእሳት ሰይፍ ከእርሱ ከቄሱ መናፍስትን አሳደዳቸው ቄሱም ወደ መቅደስ በገባ ጊዜ መቀደሻውን የክህነት ልብስ ለበሰ ሁለመናውም እንደ እሳት ሆነ ቀድሶም ለሕዝቡ ሥጋውንና ደሙን አቀበላቸው።
ልብሰ ተክህኖውንና የመቀደሻውን ሽልማት ከላዩ አውልቆ ወደ ውጭ በወጣ ጊዜ እንዚያ የጠቆሩ መናፍስት ርኩሳን ተቀብለው እንደቀድሞው አደረጉበት።

አባ ዮሐንስም ይህን ነገር ለመነኰሳቱ ሲያስረዳ እንዲህ አላቸው በቅዳሴ አገልግሎት ጊዜ ለኃጢአተኛውና ለጻድቁ ቄስ ልዩነት የለም ስለ ሕዝቡ እምነት ያ ኅብስት ተለውጦ የክርስቶስን ሥጋ ይሆናልና ወይኑም የከበረ ደሙን ይሆናልና።

ዳግመኛ በምሳሌ እንዲህ አላቸው በብረት በወርቅና በብር ላይ እንደሚቀረጽ እንደ ንጉሥ ማኅተም ነው። ማኅተሙም አይለወጥም እንዲሁ ከካህናትም የክህነት ጸጋ አይለወጥም እርሱ እግዚአብሔር በጊዜው ጊዜ ለሁሉም ለየአንዳንዱ እንደሠራው ይከፈለዋል እንጂ።

ይህንም የከበረ ዮሐንስ ታላቅ መከራ ደርሶበታል አረማውያን በርበር ማረከው ወደ አገራቸወደ ወስደውታልና እያሠቃዩትም በእነርሱ ዘንድ ብዙ ዘመን ታሥሮ ኖረ ከዚህም በኋላ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ገዳሙ መለሰው።

ከመሞቱ በፊት የሚሞትበትን ጊዜ አውቆ መነኰሳቱን ሰበሰባቸውና የወንጌልን ትዕዛዝ ይጠብቁ ዘንድ በሰማያዊ መንግሥት በጎ ዕድልን ርስትንም ከእርሳቸው ጋር ይቀበሉ ዘንድ እንደ ቅዱሳን አባቶች አካሄድ እንዲጓዙ አዘዛቸው።

ከዚህም በኋላ ጥቂት ታመመ ነፍሱን ሊቀበሉ የቅዱሳንን አንድነት ሲመጡ አያቸውና ፈጽሞ ደስ አለው ነፍሱንም በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ መነኰሳቱ ወደ ከበረች ቤተ ክርስቲያን ተሸክመው ወስደው በመዘመርና በታላቅ ምስጋና ገንዘው ቀበሩት እርሱንም ከመውደዳቸው የተነሣ ከተገነዘበት ልብስ ቆርጠው በእነርሱ ዘንድ አኖሩት ለሚታመም ሁሉ የሚፈውስ ሆነ የዚህም አባት ዕድሜ ዘጠና ዓመት ሆነ በግቢግ የሚልዋት መኖሪያው እስከ ዛሬ አለች።


#አባ_ዮሐንስ_ብጹዕ

በዚህችም ቀን ደግሞ የተመሰገነ የአባ ዮሐንስ የዕረፍቱ መታሰቢያ ነው ይህም ተጋዳይ የምንኲስና ልብስን ከለበሰ ጀምሮ የትንቢትና በሽተኞችን የመፈወስ ሀብት ተሰጠው ዜናውም በሀገሩ ሁሉ ተሰማ።

ይህን አባ ዮሐንስን ሁል ጊዜ የሚጐበኘው አንድ መኰንን ነበረ የመኰንኑም ሚስት ወደ አባ ዮሐንስ ዘንድ እንዲወስዳት ባሏን ታምለውና ታስገደድው ነበር እርሱም የከበረ አባ ዮሐንስ ከአርባ ዓመት ጀምሮ የሴቶችን ፊት አላየም አላት። ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሒዶ ሚስቱ ያለችውን ለአባ ዮሐንስ ነገረው አባ ዮሐንስም በእግዚአብሔር ፈቃድ የፈለገችውን እፈጽምላታለሁ አለው።

በዚያችም ሌሊት የከበረ ዮሐንስ ለዚያች ሴት በሕልም ተገልጾ እንዲህ አላት ጻድቅ ያልሆንኩ ወይም ነቢይ የኔን ፊት ታዪ ዘንድ የምትሺ አንቺ ሴት ከእኔ ምን አለሽ እኔስ ካንቺ ምን አለኝ እንግዲህስ ፊቴን ማየት አትሺ ይህንንም ብሎ በላይዋ ጸልዮ ባረካት።

በማግሥቱም የከበረ አባ ዮሐንስ በመንፈስ እንደታያት ለባሏ ነገረችው። መልኩንና አምሳያውን አመለከተችው ከዚህም በኋላ ከብዙ ሙገሳና ምስጋና ጋር ባሏን ወደ አባ ዮሐንስ ላከችው።

የከበረ ዮሐንስም ባሏን በአየው ጊዜ ፈገግ ብሎ የሚስትህ ምኞቷ የተፈጸመላት አይደለምን በዚች ዕለት በእግዚአብሔር ፈቃድ አግኝታኛለችና አለው መኰንኑም ሰምቶ ከትሩፋቱና ከደግነቱ የተነሣ እጅግ አደነቀ።ይህም አባ ዮሐንስ ጭንቅ በሆነ ተጋድሎ ዘጠና ዓመት ያህል ኖረ ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ።


#ቅዱሳን_ኮርዮንና_ፊልሞና

በዚህችም ዕለት የመኰንኑ አርያኖስ የጭፍሮቹ ታላላቆች ኮርዮንና ፊልሞና ከእርሳቸውም ጋር ካሉ አርባ ወታደሮች ጋር በሰማዕትነት ሞቱ።

የሰማዕትነታቸውም ምክንያት የአክሚም ታላላቆች ከሆኑ ከሰማዕታት ዲዮስቆሮስ ከሰከላብዮስና ከብኑዲያስ የተደረገውን ተአምራት በአዩ ጊዜ የወታደርነት የማዕረግ ሽልማታቸውን ጣሉ በመኰንኑ አርያኖስም ፊት ቁመው እኛ በእውነተኛ አምላክ በክርስቶስ የምናምን በግልጥ ክርስቲያን ነን ብለው ጮኹ። መኰንኑም ከእሳት ማንደጃ ውስጥ ይጥሏቸው ዘንድ አዘዘ ራሳቸውንም ሲወረወሩ ብዙዎች አዩአቸው ገድላቸውንም እንዲህ ፈጸሙ።


#አባ_ዘካርያስ_ገዳማዊ

በዚህችም ዕለት ተጋዳይ የሆነ ዘካርያስ አረፈ። ይህም ቅዱስ ከመመንኰሱ በፊት በጐዳና ሲጓዝ አረማውያን በርበር ተነሡበትና ያዙት ሊያርዱትም ወደዱ በእግዚአብሔርም ፈቃድ የገዳሙ አለቃ በዚያት ጐዳና ሲያልፍ በላያቸው ጮኸ እነርሱም ሠራዊት እንደደረሰባቸው ተጠራጠሩ ፈርተውም ሸሹ ሲሸሹም ከባሕር ገብተው ሰጠሙ።

ዘካርያስም ከመገደል በዳነ ጊዜ ይሸጥ ዘንድ ገንዘባቸውን ይዞ ወደ ከተማ ገባ የሀገሩም ገዥ ያዘው ሌባ እንደ ሆነ አስቦ ሊገለው ወደደ ግን ሥራውን በአወቀ ጊዜ ተወው።

ከዚህም በኋላ ወደ አባ ጳኩሚስ ገዳም ሒዶ የምንኲስናን ልብስ ለበሰ ሰይጣንም እስከ ቀናበት ድረስ በጾምና በጸሎት ተጠመደ ከዚህም በኋላ በአባቱ ተመስሎ በሕልም ታየውና መሞቻዬ ጊዜ ደርሷልና ትቀብረኝ ዘንድ ና አለው ቅዱሱም እውነት እንደሆነ አስቦ ወደ አባቱ ሔደ ግን በጤንነት አገኘው። የሰይጣን ተንኰልም እንደሆነ አውቆ ወደ መኖሪያው ተመለሰ ሰይጣንንም ድል እስከአደረገው ድረስ በሩን ዘግቶ እየተጋደለ ኖረ።

በሆሣዕናም ዕለት ወደ አበ ምኔቱ ሒዶ ወደ ኢየሩሳሌም ለመሔድ ፈቃድ ለመነው ፈቀደለትም በማግሥቱም ፊታቸው የሚያባራ ሦስት ሰዎች ሲጠብቁት አገኛቸውና አብሮዋቸው ሔደ።

ከዚህም በኋላ አበ ምኔቱ የአባ ዘካርያስን ቤት ሊጎበኝ ሔደ ሦስት ታላላቅ ዘንዶዎችም በምድር ላይ ሲርመሰመሱ አግኝቶ በአያቸው ጊዜ ፈራቸው እነርሱም በስሙ ጠሩት ወደነርሱም ዘወር ሲል አባት ሆይ ሲመግበን የነበረ ጌታችን ዘካርያስ ከዚህ ወደየት ሔደ ብለው በሰው አንደበት ተናገሩት። አበ ምኔቱም ሰምቶ አደነቀ መብልንም ሰጣቸው።

አባ ዘካርያስም ወደ መኖሪያው ተመልሲ በብዙ ተጋድሎ ኖረ። ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ታኅሣሥ)

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Jan, 22:48


🌹#ታኅሣሥ_29🌹

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን
#የጌታችንና_የመድኃኒታችን_ኢየሱስ_ክርስቶስ #ከእመቤታችን_ከከበረች_ድንግል_ማርያም ተወለደ፣ #ጻድቁ_ካህኑ_ንጉሥ_ቅዱስ_ላሊበላ ተወለደ፣ ከኤፍሬም ወገን #መስፍኑ_ኢያሱ ተወለደ፣ #ጻድቅ_ንጉሥ_አቃርዮስ አረፈ፣ ገመላዊው #ቅዱስ_ቆሪል አረፈ፣ #የአክሚም_ሰማዕታት መታሰቢያቸው ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ልደተ_ክርስቶስ

ታኅሣሥ ሃያ ዘጠኝ በዚህች ቀን የከበረና የተመሰገነ ታላቅ የልደት በዓል ሆነ የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም የተወለደባት ዕለት ከበዓላት ሁሉ ተለይታ ከፍ ከፍ ያለች ናት።

የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን የከበረ የልደትን በዓል በሁለት ቀኖች ያከብሩ ዘንድ በምክራቸው ተስማሙ ከወደኋላ ባለ በሃያ ስምንት ሌሊቱ የልደት በዓል ነው በሃያ ዘጠኝ መዓልቱ ጳጉሜን ስድስት በሆነ ጊዜ በዚያች ዓመት የልደት በዓል በሃያ ስምንት በመዓልት ይከበራል። ጳጉሜን አምስት ከሆነ ግን በሃያ ዘጠኝ ይሆናል ስለዚህ የበዓላት ሁሉ ራስ የሆነ የከበረ የልደት በዓል በሁለቱ ቀኖች እንዲከበር አዘዙ ወሠኑ።

የበዓላት ራስ ስለሆነ ስለ ከበረ የልደት በዓል የከበረ ወንጌል እንዲህ አለ። በንጉሡ በኄሮድስ ዘመን በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ጌታ ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ እነሆ የፍልስፍና ሰዎች ከምሥራቅ መጥተው ወደ ኢየሩሳሌም ደረሱ። ኮከቡን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው እያሉ።

እሊህ ፈላስፎች ከበለዓም ወገን ናቸው እነርሱም በከዋክብት የሚፈላሰፉ ናቸው በመጽሐፋቸው በበለዓም መጽሐፍም የአይሁድ ንጉሥ ሊወለድ እንዳለው ተጽፎአል እርሱ በለዓም ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል ከእስራኤልም ንጉሥ ብሎ ነበርና።

ይቅር ባይ እግዚአብሔርም በረቀቀ ጥበቡ አለበማቸው በሚያምኑበትም ሳባቸው እነርሱ ከዋክብትን በመጠባበቅ የሚፈላሰፉ ናቸውና ይህንንም ኮከብ ገለጠላቸው በአዩትም ጊዜ ደስ አላቸው መልኩ በብዙ አይነት ልውጥ ነውና። ሕፃን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን ይመስላል እርሱም በቀን ይጓዛል በሌሊትም ይሠወራል ከሰውም ሲገናኙ ይሠወርና ሲቆሙ በሌላ አንጻር ይገለጥላቸዋል።

እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ያ ኮከብ ተሠወራቸው እጅግ አዘኑ የሚያደርጉትንም አላወቁም ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብተው ስለተወለደው ንጉሥ ጠየቁ። የእሊህም ሰዎች ቊጥራቸው ሠላሳ ሽህ ነው ነገሥታቱ ሦስት ናቸው ለየእንዳንዱ ንጉሥ ዐሥር አሥር ሽህ ሠራዊት አለው።

ንጉሡ ኄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች። የካህናት አለቆችና የሕዝቡን ጸሐፊዎች ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስ በየት ይወለዳል ብሎ ጠየቃቸው። በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ነው አሉት በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና።

የኤፍራታ ዕፃ ቤተልሔም አንቺም ከይሁዳ ነገሥታት አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ካንቺ ይወለዳልና። ከዚህም በኋላ ኄሮድስ ሰብአ ሰገልን በጭልታ ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከነሱ ተረዳ።
ሒዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር እርግጡን መርምሩ ያገኛችሁትም እንደሆነ እኔም መጥቼ እሰግድለት ዘንድ በኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ ብሎ ወደ ቤተልሔም ሰደዳቸው። የነገራቸውንም ሰምተው ከንጉሡ ሔዱ እነሆ በምሥራቅ ያዩት ከከብ ወደ ቤተልሔም እስኪያደርሳቸው ይመራቸው ነበር ሕፃኑ ካለበትም ዋሻ ላይ ደርሶ ቆመ።

ኮከቡንም ባዩ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር አገኙት ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ ከርቤ ዕጣን እጅ መንሻ አቀረቡለት።

በእግዚአብሔርም ፈቃድ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑ ጌታ ኢየሱስም በዚያች ዕለት ወደ ቤተልሔም መጡ ስለዚህም ሰብአ ሰገል አገኙአቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ናዝሬት በሌላ ቦታ አላደገምና ከተወለደም ዕድሜው ሁለት ዓመት ሆኖት ነበር።

አምላክ ነውና ስለ መንግሥቱ ወርቅን ገበሩለት ክህነትም ገንዘቡ ነውና ዕጣንን ገብሩለት ማሕየዊ ለሆነ ሞቱ ምልክትም ከርቤን ገበሩለት። ወደ ኄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራቸው በሌላ መንገድም ወደ አገራቸው ተመልሰው ገቡ። አምላክ በሥጋ ስለመገለጡ ዓዋጅ ነጋሪዎችና ሰባኪዎች ሆኑ።

ይችም ዕለት ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ስለርሷ የተናገረላት ናት እንዲህ ብሎ እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅን ትወልዳለች ስሙንም ዐማኑኤል ትለዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው።

ስለዚችም የከበረች ድንግል ነቢይ ሕዝቅኤል እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ እግዚአብሔርም አለኝ ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች አትከፈትም የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር አለ።

ነቢዩ ዳንኤልም አለ ሌሊት በራእይ አየሁ እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ ዘመኑን ወደ ሚያስረጅ ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት የዘላለም አገዛዝ ጌትነት መንግሥት ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው።

ዳግመኛም ኢሳይያስ እግዚአብሔር እንደ እኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጸልኝ አለ። አሁንም ደግሞ አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ አለ ሁለተኛም ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል አለ። ዳግመኛም ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶልናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው። ስሙም ድንቅ መካር የዘላዓለም አባት የሰላም አለቃ ይባላል አለ።

ኤርምያስም አለ እግዚአብሔር እንዲህ አለ በዚያን ወራት ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ በምድርም የቀና ፍርድን ያደርጋል እግዚአብሔርም ያመኑበትን ያድናቸዋል።
ኤልሳዕም እንዲህ አለ።እ ግዚአብሔር ከሰማይ ይወርዳል በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ ዕውነትን ያስተምራቸዋል ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆኑ ወገኖች በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል። ናሆም ነቢይም እንዲህ አለ። እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል ልብሱም እንደልብሴ ነው።

ነቢዩ ኢዩኤልም እንዲህ ተናገረ የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር ስለርሷም ይቺ ማን ናት ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይህች ድንግል ናት በርሷም የተጐሳቈሉ አሕዛብ ይድናሉ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት።

ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ አለ እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ ዛሬም በተዋሕዶ ወለድኩህ አለኝ። ለምነኝ አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው። ዳግመኛም አብ አለ ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ካንተ ጋራ ሳለሁ ከአጥቢያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ የዓለሙ አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ ከማለም አይጸጸትም።
ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደተገኘ ለእስራኤልም በበረሀ ውስጥ ከኅቱም አለት ውኃ እንደ ፈለቀ የደነቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደ አፈራች። በሶምሶንም እጅ ውስጥ ከአህያ መንጋጋ ዐጥንት ውኃ እንደ ፈሰሰ።

እንዲሁ የጌታችን ልደት በኅቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደ ነደደች ዕፂቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁ የመለኮቱ እሳት ድንግልን አላቃጠላትም።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Jan, 22:48


#ጻድቁ_ካህኑ_ንጉሥ_ቅዱስ_ላሊበላ

በዚህች ዕለት ቅዱስ ላሊበላ ከአባቱ ከዐፄ ዛን ስዩም ከእናቱ ከልዕልት ኪሪዮርና በ1101ዓ.ም ታኅሣሥ 29 ቀን በቤተ መንግሥ ተወለደ። ዐፄ ዛን ስዩም ከመንገሡ በፊት የዋግ ሹም ሆኖ ሲያስተዳድር ዑጽፍት ወርቅ የምትባል ሴት አግብቶ ንጉሥ ቅዱስ ገብረ ማርያምና ዮዲት የምትባል ልጅ(ርብቃም) የሚሉ አሉ ከወለደች በኋላ ዑጽፍተ ወርቅ ሞተች። ከዚህ በኋላ የክፍለአገር ገዥ ከሆነው ረዳኢ ከተባለው የተወለደችውን ኪሪዮርናን አግብቶ ቅዱስ ላሊበላን ወለደው። ቅድስት ኪሪዮርና ማለት ቤተ ክረሰስቲያን ማለት ነው።

ቅዱስ ላሊበላ በተወለደ ጊዜ ነጫጭ ንቦች ሰፍረውበት እንደማር ሲልሱት እናቱ ስታይ በመደንገጥ "ላል ይበላል" በማለት ተናገረች። ይህም በአገውኛ ቋንቋ ልጄን ንብ በላው ማለት ነው። በዚህ መሰረቴ ላልይበላል ተብሎ እየተጠራ እንደሠ ከጊዜ ብዛት ላሊበላ ተብሏል። በነገራችን ላይ የተሳሳተ ትርጉም የያዙ አላዋቂዎች ላሊበላ ማለት ለማኝ እንደሆነ አድርገው በአንዳንድ አካባቢዎች ይናገራሉ። ላሊበላ ማለት ግን ጣፋጭ የንስሃ ጋሻ የጽድቅ አባት ማለት ነው እንጂ ለማኝ ለፍላፊ ማለት አይደለም።

ከዚህም በኋላ እናትና አባቱ ልጃቸው ወደፊት ንጉሥ ሆኖ ብዙ ሰራዊት የሚከተለው ትልቅ ሰውና መንፈሰ እግዚአብሔር ያደረበት መሆኑን በንቦች መክበብ በመረዳታቸው በ40 ቀኑ በብዙ ሺህ የሚቆጠር ሰራዊትና ካህናት ታጅበው በእልልታና በደስታ ዐፄ ካሌብ በአሰሩዋት ማይ ማርያም በተባለችው ቤተ ክርስቲያን የክርስትናውን ሥነ-ሥርዓት አስፈጽመዋል። የክርስትና ስሙም ገብረ መስቀል ተብሏል። ቅዱስ ላሊበላ በቤተ መንግሥት ውስጥ ለነገሥታት ልጆች እንደሚሰጥ እንክብካቤና ሥነ-ሥርዓት በጥበብና በሞገስ አደገ። ዕድሜውም ለትምህትተ ሲደርስ መምህር ተቀጥሮለት ከፊደል እስከ ዳዊት የሚሰጠውን ትምህርት ያለማዳገም ከፈጣሪ በተሰጠው ፀጋ በአጭር ጊዜ ውስጥ ተማረ። በዚህም ላይ እንዳለ የበለጠ ፈጣሪውን ማገልገል በመፈለጉና በመምረጡ ቤተ መንግሥቱን ትቶ ትምህርቱን ለማሻሻል ወደ ምድረ ጎጃም ሄዶ አሉ ከተባሉ መምህራን በተለይም መምህር ኬፋ ከተባሉ ምሁር አጠቃላይ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ተምሮ ወደ ደብረ ሮሃ ተመልሶ ሥርዓተ መንግሥትን ወንድሙ ቅዱስ ገብረ ማርያም እያስተማረው ሳለ ለምቀኝነት የሚያርፈው ሰይጣን በንጉሥ ባለሟሎች(አማካሪዎች) ላይ አድሮ የሁለቱን ፍቅር በጠሰው። ሰዎቹ ወደ ንጉሥ ቀርበው "ንጉሥ ሆይ ሺህ ዓመት ንገሥ እነሆ ላሊበላ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅነትን በማግኘቱ አስተባብሮ ንጉሥነትዎን መንግሥቱ ሊቀማዎት ነውና እወቁበት" በማለት ነገሩት። ንጉሡም በነገሩ እጅግ ተቆጥቶ ወደ ማረፊያ ቤቱ ገብቶ እንጀራ አልበላም ውሃም አልጠጣም ብሎም እንደ ንጉሥ ዓክአብ ተጨንቆ ተጠቦ ሳለ እህቱ "ንጉሥ ሆይ ልብህ አይዘን አትጨነቅ ነገሩን ለእኔ ተወው" ብላ አረጋጋችው። ላሊበላ ግን ይህን ሁሉ ነገር አላወቀም ነበርና በንጹህ ልቦናው በቤተ መንግሥቱ እንደ ተቀመጠ ከዕለታት አንድ ቀን ኮሶ ታይቶት መድኃኒት እንድታጠጣው ቂመኛ እህቱን ጠየቃት እሷም የምታጠምድበትንና የምትገድልበትን ስታስብና ስትፈልግ ስለ ነበር ይህን አጋጣሚ በማግኘቷ ሀሳቡን ደስታ ተቀብለችውና ኮሶውን አዘጋጅታ መርዝ ቀላቅላ አቀረበችለት። ከእርሱ ጋራ የሚኖር የማለየው አንድ ዲያቆን ነበር። በባህሉም መሠረት ዲያቆኑ ቀምሶ ስለሚሰጥ ያንን ሲቀምሰው አስታወኮት ሞተ። የዲያቆኑንም ትውኪያ አንድ ውሻ በመላሱ ሞተ። ከዚህም በኋላ ላሊበላ መንፈሱ ታወከ። ከባድ ሀዘንም አደረበት። "እናንተ ንጹሐን ለእኔ በታዘዘው መቅሰፍት በመሞታችሁ እኔም የእናንተን መንገድ እከተላለሁ እንጂ ወደ ኋላችሁ ቀርቼ ነፍስ ገዳይ አልሆንም" አለና በውስጡ ፍቃደ እግዚአብሔር ስላለበት ፈጣሪ ሚስጥር ሊገልጽለት በመፍቀዱ በጽዋው የተረፈውን መርዝ አንስቶ ጠጣው። እርሱም ወዲያው ተዘረረና ወደቀ። በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት መጥተው ነፍሱን ወደ ፈጣሪ ወስዷት። ሥጋው ግን ሙቀት ስላልተለየው ሰዎች ለመቅበር ቢሞክሩ እንደእሳት እየፈጃቸው ሦስት መዓልትና ሌሊት በሚደንቅ ሁኔታ ተቀመጠ።

ቅዱሳን መላእክት ሰባቱን ሰማያት አንድ በአንድ እያሳዩ ወደ ፈጣሪ ነፍሱን ከአቀረቧት በኋላ እግዚአብሔር አምላክ "ወዳጄ ላሊበላ ሆይ የጠራሁህ እኔ ነኝ በማለት ወሰን የሌለውን ፍቅሩን ከገለጸለት በኋላ ሀይሉንና ጥበቡን በእርሱ ላይ አሳድሮ "ከከርሰ ምድር አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚያንጽና በኢትዮጵያ አገር ላይ አርባ ዓመት እንደሚነግሥ ሕዝበ እግዚአብሔር ድንቅ ሥራውን በመመልከት ድኅነትን፣ በረከትን፣ ፀጋን፣ እንደሚያገኙ በተለይም የኢትዮጵያ ሕዝቦች ኢየሩሳሌምን ለማየትና ለመሳለም ሲሔዱ የሚደርስባቸው መከራና ሞት ደማቸው ከፊቴ በመጮሁ በእርሱ ሥራ ኢየሩሳሌምን እንደሚያንፅና ለምን እንደሚሰራ ጥቅሙን በመግለጽ ይሰራ ዘንድ መመሪያ ሰጠው። ቅዱስ ላሊበላ ግን ይህን ማድረግ እንማይቻለው ቢገልጽም አምላክ ከእርሱ ጋራ እንደሚሆን ብቻ "ስሙ በአንተ ይሁን እኔ ነኝ የምሰራው" በማለት ገለጸለት። ከላይ እንደተገለጸው በድኑ መንፈስ ቅዱስ ሳይለየው እንደ እሳት ሰዎችን እየፈጃቸው ተጨንቀው ተጠበው በሁኔታው በመገረም ለሦስት ቀንና ሌሊት እንዳሉ በሦስተኛው ቀን ነፍሱ ከሥጋው ተዋሕዶ ተነሳ።

ቅዱስ ላሊበላም ከሰው ተለይቶ ከዘመድ ርቆ የሰው ድምጽ ከማይደርስበት ቦታ ሄዶ ሌት ከቀን በመጸለይ በጾምና በጾሎት ተወስኖ ከአምላኩ ጋር በበለጠ ግንኙነቱን እያጠናከረ እንዳለ አንድ ቀን ፈጣሪ ቅዱስ ገብርኤልን ላከውና መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልም ላሊበላን "የእግዚአብሔር አገልጋይ ላሊበላ ሆይ ሰላም ለአንተ ይሁን እንሆ እግዚአብሔር አምላክ በኢትዮጵያ ላይ ካህንና ንጉሥ ሆነህ ሰዎችን ለመንግሥተ ሰማያት የምታበቃ ነህና በህገ አብርሃም ትወሰን ዘንድ ወዳንተ መጣሁ ስለሆነም ነገ በአሁኑ ሰዓት የምትመጣ በድንቅ ሥራዋ አምላክን ያስደሰተች አንዳንተ የተመለጠች ቅድስት ሴት ትመጣለችና እርሷን አግብተህ ልጅ ትወልዳለህና በሚያስደስት ቃል ተቀበላት" አለው። ቅዱስ ላሊበላ ግን ፍቃዱ እንዳልሆነ ቢገልጽም የእግዚአብሔር ትዕዛዝ እንደሆነ በድጋሚ ሲነግረው ቃሉን ተቀበለው። እንደተባለውም በማግስቱ ቅድስት መስቀል ክብራ እንደ ብርቱካን፣ መዝ፣ የመሳሰሉትን ፍራፍሬዎች ይዛ ወደ ቅዱስ ላሊበላ ሄደች እርሱም በደስታ ተቀበላት። ከዚያም ነገረ እግዚአብሔርን ተነጋግረው ወደ ቤተሰቦቿ ወሰደችው። ለቤተሰቦቿ መላኩ በህልም ነግሯቸው ስለነበር በደስታ ተቀበሉት። በዚያም በፈቃደ እግዚአብሔር በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻቸውን ፈጽመው በጾምና በጸሎት ተወስነው በመኖር ላይ ሳሉ ለምቀኝነት የማያርፈው ሰይጣን አሁንም ፈተናውን አዘጋጅቶ ሶስናን በሐሰት ዝሙትን ፈጽማለች ብለው እንደወነጀሏት ሁሉ ቅዱስ ላሊበላንም "ከቤተ መንግሥት ጠግቦ ወጥቶ የሰው እጮኛ ያባልጋል" በማለት ለንጉሡ ሹክተኞች ነገሩት። ንጉሡም ወታደሮችን ልኮ አስመጣውና ቀኑም ዐርብ ቀን በመሆኑ እንዲገረፍ አዝዞ ወደ ቅዳሴ ሄደ። ዘጠኝ ሰዓት ላይ ወደ ቤቱ ሲሄድ የጅራፍ ጽምጽ በመስማቱ "ምንድነው? የሚሰማው" ብሎ ባለሟሎቹን ሲጠይቃቸው "ቅዱስ ላሊበላ እየተገረፈ ነው" አሉት ንጉሡም ወዲያውኑ እንዲያመጡለት አዘዘ። ሲመለከተውም በሰውነቱ ላይ ምንም የግርፈት ምልክት አላየበትም ንጉሡም ጻጽቅና እውነተኛ መሆኑን ፈጣሪም ከግርፋትና ከጥፍት ከልሎታልና "እንኳን ስ ሊሞት ግርፋቱ አልተሰማውም" በማለት እጅግ አደነቀ። ከባድ ሀዘንም ተሰማው። አምላኬን በድያለሁ የማይገባ ሥራ ሰርቻለሁ "ብሎ ቅዱስ ላሊበላ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Jan, 22:48


ቅዱስ ላሊበላ ሥራውን ከዚህች ቦታ እንደሚጀምርና መጀመርያ የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን እንደሚሰራ አወቀ በዚህም መሰረት በመጀመርያ ደረጃ ቤተ ማርያም ሠራ። ከዚያም ቤተ መድኃኔዓለም፣ ቤተ መስቀልን፣ ቤተ ደናግል፣ ቤተ ጊዮርጊስ፣ቤተ ገብርኤል ወቤተ ሚካኤል፣ ቤተ መርቆሬዎስ፣ ቤተ አማኑኤል፣ ቤተ አባ ሊባኖስ። እነዚህን ቤተ መቅደሶች መንፈስ ቅዱስ ጥበብን ገልፆታልና ግድግዳውን፣ ጣራውን፣ በሩንና መስኮቱን፣ አእማዱን ቅኔ ማህሌቱን ልዩ ልዩ ቅርፅ እያመጣ እያስጌጠና እያሳመረ ከመላዕክት ጋር አመቤታችን እየተራዳችው በ23 ዓመት በዚህ አጭር ግዜ ውስጥ እነዚህን አስደናቂ ቤተ መቅደሶች ሰርቶ አጠናቀቀ።

ቅዱስ ላሊበላ የአነፃቸው አብያተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ በውጭም አገር ብዙ እንደሆኑ ታሪኩ ይገልጻል። ከብዙዎቹ ጥቂቶቹን እንደ ምሳሌ ብንመለከታቸው፦ አዲዲ ማርያም፣ አሸተ ማርያም ጀምሮ ነበር፣ ሶማርያ መቅደስ ማርያምን (መቃዲሾ ውስጥ) ብዙ የተጀመሩና ተሰብስበው አገልግሎት የሚሰጡ በኢትዮጵያ ብቻ 23 እንደሚደርሱ ታሪክ ያወሳል።

ቅዱስ ላሊበላ መዋዕለ ዘመኑን በሰላም፣ በፅኑ፣ በእምነት፣ በፍቅርና በአንድነት ከአሳለፈ በኋላ ንግስናውን ለወንድሙ ልጅ እንዲሁም ለአሳደገውና በረከቱን ለሰጠው ለቅዱስ ነአኵቶ ለአብ አስረክቦ በጾም በፀሎት ተወስኖ ኖረ። ከዚህም በኋላ የሚያርፍበት ጊዜ ሲደርስ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በብርሃን ሠረገላ ተቀምጦ የሚአስፈራ መብረቅን ተጐናጸፎ አእላፋት ሠራዊቶቹ ዙሪያውን ሁነው ወደርሱ መጥቶ እንዲህ አለው "ወዳጄ ላሊበላ ሆይ ሰላም ይሁንልህ እኔ በማይታበል ቃሌ እነግርሃለሁ ማደሪያህ ክብርር ሁሉ ከከበሩ ዐሥራ ሁለቱ ሐዋርያቶቼ ጋራ ይሁን። በጸሎትህና በቃልኪዳንህ ለሚታመን እምነቱ እንደ ቅዱሳን ጴጥሮስኔ ጳውሎስ ደም መፍሰስ ይሆንለታል።

ወደ ቤተ መቅደስህም የሔደ በኢየሩሳሌም ወዳለው ቤተ መቅደሴ እንደ ሔደ ይሆንለታል መቃብርህንም የተሳለመ የሥጋዬን መቃብር እንደ ተሳለመ ይሆንለታል በዓመታቱ ወሮች ሁሉ የተራቡትን እያጠገበ፣ የተጠሙትንም እያጠጣ መታሰቢያህን የሚያደርግ እኔ የተሠወረ መና እመግበዋለሁ የሕይወት ጽዋንም አጠጣዋለሁ። በመታሰቢያህ ቀንም ዕጣን ወይም ስንዴ የሚያገባውን እኔ በኢየሩሳሌም ሰማያዊት በውስጠኛው መጋረጃ አስቀምጬ ከተቆረሰው ሥጋዬ አቆርበዋለሁ፤ በአማላጅነትህም እየታመነ የገድልህንና የቃል ኪዳንህን መጽሐፍ የሚጽፈውን ያንተ ስም በተጻፈበት ቦታ እኔ ስሙን እጽፋለሁ፣ በፍጹም ልቡ ለሚያምን ይሁን የማይታበይ ቃል የተናገርኩ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እኔ ኢየሱስ ክርስቶስ ነኝ" አለው።

ቅዱስ ላሊበላም ይህን ቃል ኪዳን ስለ አጸናለት ክብር ይግባውና ጌታችንን እያመሰገነ በምድር ላይ ወድቆ ሰገደ። ጌታችንም ሰላምታ ሰጥቶት በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐረገ። ከዚህም በኋላ ጥቂት ሕማም ታሞ ሰኔ12 ቀን በ1197ዓ.ም በ96 ዓመቱ በሰላም ዐረፈ። ሲያርፍም ደገኛው ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ጋር ነገራተ እግዚአብሔርን እየተነጋገሩ እንዳለ ድንገት እንደ እንቅልፍ ሸለብ አድርጎት እንደሆነ ታሪኩ ይገልፃል። ነፍሱንም የብርሃን መላእክት ተቀብለው የዘላለም ሕይወት ማደሪያ ወደሆነ ማረፊያው አስገቡት። (የሰኔ12 ስንክሳርና ቅዱሳንና ድንቅ ሥራቸው የአራቱ ቅዱሳን ነገሥታት ታሪክ ከሚለው መጽሐፍ።)

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ኢያሱ_ነቢይ

በዚህችም ዕለት ከኤፍሬም ወገን መስፍኑ ኢያሱ ተወለደ እርሱም ለእስራኤል ልጆች ከጠላት ሰልፍ መድኃኒት ሁኖ ያዳናቸው ነው። የጌታችንም መወለድ ለአዳምና ለልጆቹ መድኃኒት ሆናቸው። የርሱም የቀድሞ ስሙ ሆሴዕ ነበረ እስራኤልን ከአማሌቅ ጦርነት በራፌድ በአዳናቸው ጊዜ ኢያሱ ተብሎ ተጠራ ይህም አዳኝ ማለት ነው።

ሙሴም ከሞተ በኋላ እግዚአብሔር መረጠውና ለእስራኤል መስፍን አድርጎ ሾመው ልዩ ከሆኑ አሕዛብም ጦርነት አዳናቸው ርስታቸውንም አወረሳቸው ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ጻድቅ_አቃርዮስ

በዚህችም ዕለት የሮሀ ንጉሥ አቃርዮስ አረፈ የርሱም ግዛቱ በሶርያ አገር ሰርሜን በምትባል ክፍል ነው እርሷም ሮሀ ናት።

ጣዖትን የሚያመልክ ሆኖ ኖረ መፃጉዕም ነበረ ለባለ መድኃኒቶችም ገንዘቡን ሁሉ ሰጥቶ ሊአድኑት አልቻሉም። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሽተኞችን በማዳን አጋንንትን በማስወጣት የዕውሮችን ዐይኖች በመግለጥ ሙታንን በማስነሣት የሚሠራውን ድንቅ ተአምራቱን በሰማ ጊዜ እንዲህ ሲል ወደርሱ ላከ።
የሰውን ሥጋ ለብሰህ በኢየሩሳሌም የተገለጥክ የእግዚአብሔር ልጅ ምስጋና ይድረስህ ከእርሱ ሳትለይ ወደታች ለላከህ ለቸር አባትህም ምስጋና ይድረሰው አንተ የምትስተካከለው ክርስቶስ እንደሆንክ በሕሊናየ ለገለጠልኝ መንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይሁን። ያለወንድ ዘር በድንግልና ለወለደችህም እናትህ ምስጋና ይሁን ለሚያምኑብህ ሁሉ ሰላምታ ይድረሳቸው።

እኔም በአንተ አምኜ ከንቱ ጣዖትን ከማምለክ አንተን ወደ ማምለክ ተመለስኩ በኔ ላይም ንጉሥ ትሆን ዘንድ ሀገሬንም ትባርክ ዘንድ ከበሽታዬም ታድነኝ ዘንድ ከኃጢአቴም ታነጻኝ ዘንድ ወደኔ ና ጌታዬ ሆይ የከበረ ስምህን አይሁድ ሲጠሉ ለአንተ በኢየሩሳሌም መኖር ምን ያደርግልሃል። በከንቱ ለምን ትደክማለህ መካር ያጡ ወገኖች ናቸውና በቀድሞ ዘመንም ድንቆች ተአምራቶችን በማድረግ ከግብጽ አገር በአወጣኻቸው ጊዜ አላመኑብህም በበረሀም አርባ ዓመት መናውን በመገብካቸው ጊዜ ተቆጥተህ ለጥፋት እስከ አደረስካቸው በአንተ ላይ ምን ያህል አጒረመረሙብህ በሚራብና በሚጠማ ምድራዊ ሥጋማ ሲያዩህ እንዴት ነዋ ኀሳባቸው ከዚህ የተለየ ይመስልሃልን አንተ ከጥንት ጀምሮ የተሠወረውን ታውቃለህና። ይኸንንና ይህን የመሰለውን ጽፎ ደብዳቤ ወደርሱ ላከ።

የንጉሥ መልክተኞችም ወደ ጌታችን በደረሱ ጊዜ ሳይነግሩት የሰመጡለትን መልእክት አውቆ ነጭ ልብስ አነሥቶ ፊቱን አሸበት የፊቱም መልክ ወደ ልብሱ ገባ ከደቀ መዝሙሩ ከታዴዎስ ጋር እንዲህ ብሎ ላከለት ይህን የኔ መልክ የሆነውን ሥዕል ተቀበል እርሱም የምትሻውን ሁሉ ይፈጽምልሃል ከበሽታህም ይፈውስሃል ሀገርህንም ይባርካል መንግሥትህንም ያጸናል ይህ ሥዕል እኔን ነውና ይለወጥ እንደሆነ በውኃ በእሳት ፈትነው።

መልክተኞችም ወደ ንጉሥ አቃርዮስ በደረሱ ጊዜ ያንን ሥዕል ሰጡት በእሳትና በውኃም ፈተናውና ምንም ምን ጥፋት አልደረሰበትም የሮሀ አገር ሰዎችም ከንጉሣቸው ጋር በጌታችን የመለኮት ሥልጣን አመኑ ይህ ሥዕል ቊጥር የሌለው ብዙ ድንቅ ተአምራትን አደረገ ንጉሡንም ከበሽታው ፈወሰው ከዚህም በኋላ ዕድሜውን ሲፈጽም በዚች ዕለት አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ቆሪል_ገመላዊ

በዚህችም ዕለት ሰምኑድ ከሚባል አገር ገመላዊው ቅዱስ ቆሪል አረፈ። እርሱም በጾም በጸሎት ተወስኖ የሚኖር ነው እግዚአብሔርም የተሰወሩ ምሥጢራት ማወቅን ሰጠው የሚገለገልባቸው ከማሳም ተልባ የሚጭንባቸው ሦስት ግመሎች አሉት።

ፈራጉን በሚባል አገር ለእመቤታችን ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ካህናት የሆነ አንድ ሰው ነበረ ቤተ ክርስቲያኒቱም ነገሥታትና መኳንንት በየጊዜው የሰጧት ብዙ ገንዘብ አላት በሊቀ ካህናቱም ዘንድ የዕቃው ሣጥን በሥውር ይኖር ነበር የዚያንም ዕቃ ቊጥር ኤጲስቆጶሱ ያውቃል ያ ሊቀ ካህናት በእርሱ ሥልጣን ሥር ነበርና ከዚህም በኋላ የዕቃው ሣጥን ያለበትን ለልጁ ሳይነግር ያ ሊቀ ካህናት በድንገት ሞተ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Jan, 22:48


በሕዝቡ መካከል "ከዛሬ ጀምሮ መንግሥት ለአንተ ይገባል በግፍ አስገርፌሀለሁ በድዬሀለሁም ይቅር በለኝ" በማለት ከጫማው ወድቆ ይቅርታ ከጠየቀው በኋላ መንግሥቱን አስረክቦ መንኖ ለመሔድ ወሰነ። የእግዚአብሔር መንፈስ ያደረበት ቅዱስ ላሊበላም "ለይቅር ይቅር ብብያሁ ነገር ግነ መንግሥት የእግዚአብሔር ገንዘብ ናትና መንግሥትህን የምቀበለው ከእግዚአብሔር እንጂ ከአንተ አይደለም አንተም በዙፋንህ መቆየት አለብህ እኔ ግን መልካም ፈቃድ ከአምላኬ እስካገኝ ድረስ እጠይቃለሁ" ብሎ የዐፄ ገብረ ማርያም ጫማ ስሞ በፍቅር ተሰናብቶ ወጣ። በዚህ ጊዜ ሕዝቡና "መንግሥትን ያህል ነገር እንደ ቀላል ነገር ቆጥሮ አልነግሥም ብሎ በመሄዱ እንዴት የእግዚአብሔር መንፈስ ቢያድርበት ነው?" በማለት በችሎት ተቀምጦ ሁኔታውን በግብር ሲከታተል የነበረው ሁሉ እያለቀሰ ቅዱስ ላሊበላን ተከትሎ ወጣ። ቅዱስ ላሊበላ ግን በአላማው ፀንቶ በሰዎቹ ፍቅር ሳይታለል እግዚአብሔር የሰጠውን ረዳቱን ቅድስት መስቀል ክብራን ይዞ ወደ አክሱም ሄደ።

በአክሱም አካባቢ በአባ ጰንጠሌዎን ገዳም በጾምና በጸሎት ተወስነው ፈጣሪያቸውን እየተማፀኑ ሳለ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ መጥቶ "ሰማያዊ ኢየሩሳሌምን እንዳየህ ምድራዊት ኢየሩሳሌምንም አይቶ ህንፃ ቤተ መቅደሱን በሰማያዊትና በምድራዊት ኢየሩሳሌም አምሳል ያንፅ ዘንድ ኢየሩሳሌም ሔዶ የተወለደበት ቤተልሔም፣ የተጠመቀበትን ዮርዳኖስ፣ የተሰቀለበትን ቀራንዮ፣ የተቀበረበትን ጎልጎታን፣ ደብረ ታቦርን ምስጢረ መለኮቱን የገለጸበትን አጠቃላይ ብዙ ተአምራት ያደረገበትን ሁሉ እንዲያይና እንዲሳለም መልአኩም እንደሚመራው መስቀል ክብራ ግን በዚሁ ከደናግሎች ጋር እንደምትቀመጥና ቅዱስ ሚካኤል እንደሚያጽናናት እንደሚጠብቃት መታዘዙን ነገረው።

በዚህም መሠረት ቅዱስ ላሊበላ ወደ ኢየሩሳሌም በፈቃደ አምላክ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ጠባቂነት በሱዳንና በግብጽ አድርጎ ኢየሩሳሌም ገባ። በዚያም ከላይ የተጠቀሱትን ቅዱሳን መካናትንና ሌሎችንም ቅዱሳት ስፍራዎች ለዐሥራ ሦስት ዓመታት በመዘዋወር ተመለከተ። ከዚህ በኋላ ቅዱስ ላሊበላ የጉብኝቱንና የተፈቀደለትን ጊዜ ሲፈጸም አሁንም መልአኩ ተገልጾ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሶ ሄደ መንግሥትን ከዐፄ ገብረ ማርያም ተረክቦ የታዘዘውን እንዲሰራና በመንገድ በግብጽ ምድር የተበተኑትን ወገኖችን ወደ ኢትዮጵያ ይዞ እንዲሄድ የታዘዘ መሆኑን ገለጸለት። ቅዱስ ላሊበላም በፈቃደ አምላክ በግብጽ ያሉትን ክርስቲያኖች ሰብስቦ በጊዜው የነበረው የግብጽ መንግሥት የእስላም ሃይማኖት ተከቲይ በመሆኑ እንዴት አድርጎ እንደሚያስተዳድራቸው ጠየቃቸው። ክርስቲያኖቹም እግዚአብሔርን ማምለክ እንደተከለከሉና በሀዘን በሰቀቀን የሚኖሩ መሆናቸውን ገለጹለት። በዚህ ዘመንም በመካከለኛው ምሥራቅ 3ኛው የመስቀል ጦርነት በመኖኑ ግብጻውያን ፊታቸውን ወደዚያ አዙረው ስለነበር ቅዱስ ላሊበላ በፈቃደ አምላክ በርካታ ክርስቲያኖችን ይዞ ወደ ኢትዮጵያ መጣ።

ዐፄ ገብረ ማርያም ወንድሙ ቅዱስ ላሊበላ ሕዝበ ክርስቲያንን ይዞ የኢትዮጵያ ምድር እንደረገጠ በሰማ ጊዜ በክብር የሚቀበሉት ቁጥር ስፍር የሌላቸው ሰራዊት አሰልፎ ወደ ቤተ መንግሥቱ እንዲመጣ ላከበት። ቅዱስ ላሊበላም ከባለቤቱ ጋር እና ከሕዝቡ ጋር በአክሱም ስለነበር የእግዚአብሔር ፍቃድ እንደሆነና ጊዜም እንደደረሰ በማወቁ ልዋል ልደር ሳይል ወደ ቤተ መንግሥቱ መጥተ ከዐፄ ገበረ ማርያም ጋር ተገናኘ። ንጉሡ ዐፄ ገብረ ማርያም ቅዱስ ላሊበላ ወደ እርሱ መምጣቱን በሰማ ጊዜ በፍቅር እንባ ተቀበለውና ሕዝቡን ሰብስቦ አዋጅ ነግሮ "እንሆ የአምላክ ፈቃድ ደርሷል መንግሥት ለዚህ ቅዱስ ሰው ይገባል ብሎ ዙፋኑን ለቅዱስ ላሊበላ አስረክቦ ተሰናብቶ ዛሬ ቅዱስ ሐርቤ እየተባለ ወደሚጠራው ገዳም ዘግቶ በጾም፣ በጸሎት፣ በቀኖናና በንስሐ ሰውነቱን ለፈጣሪው አስገዝቶ በክብር የካቲት16 ቀን ዐርፎአል።

ከዚህ በኋላ ቅዱስ ላሊበላ ንጉሥ ነኝ ብሎ ሳመካ ስልጣኑን ለሕዝቡ በመስጠት ሕዝቡን ይመራ ነበር። ሕዝቡም የቅዱስ ላሊበላን የሃይማኖት ጽናትና ደግነት እያየ "ይህን ጻድቅ ንጉሥ ዕድሜውን አርዝምልን" እያሉ ይጸልዩለት ነበር። የቅዱስ ላሊበላን ደግነት በኢትዮጵያ የሚኖሩ ሕዝቦች ብቻ ሳይሆኑ በውጭም ያሉ ነገሥታትና ሕዝብ ጭምር ያውቁ ነበር በዚህም መሰረት እስላሙም ክርስቲያኑም ቅዱስ ላሊበላን አንስተው አይጠግቡም ነበር። በቅዱስ ላሊበላም ዘመነ መንግሥት ጊዜ ኢትዮጵያ በውጭው ዓለም ያላት ግንኙነት የሰላም፣ የፍቅር፣ የክብርና የደስታ ግንኙነት ነበራት ለዚህም ነበር 1189ዓ.ም አካባቢ ሳላህ አዲን የተባለው የእስላም ንጉሥ በሦስተኛው የመስቀል ጦርነት ኢየሩሳሌምን በያዘ ጊዜ ከክርስቲያን ቅርሶች ዋና ዋናዎቹን በጎልጎታ በሚገኘው በጌታችን መቃብር አጠገብ ያለውን ዕሌኒ ንግሥት ቅዱስ መስቀሉን ያስወጣችበት ዋሻና በቤተልሔም ጌታ የተወለደበትን ጎል (በረት) ለቅዱስ ላሊበላ በስጦታ ያበረከተው።

የቅዱስ ላሊበላ ቤተ መቅደሶች አሰራርና ፍጻሜ፦ ቅዱስ ላሊበላ በዘመኑ ይህን ድንቅ ሥራ የሰራው ጮማ በመቆራረጥ ጠጅ በማማረጥ ልብስ መንግሥትን ለብሶ በመሽሞንሞን አልነበረም። ለአንዲት ደቂቃ መንፈስ እግዚአብሔር ያልተለየው ቅዱስ አባት ነበር። ፈጣሪው የሚመሰገንበትን የእርሱም ስም ለዘላለም የሚጠራበትን ቤተ መቅደስ ለማነፅም ሱባኤ ገብቶ ቦታው የት እንደሆነ ተረዳ። ነገር ግን የተገለጸለት ቦታ ቀይት የምትባል ባላባት ትኖርበት ነበር። ንጉሥ እንደመሆኑ መጠን ሌላ ቦታ ሰጥቶ መጠቀም ይችል ነበር። ግን የትሕትና አባት ነውና መብቷን ሳይነካ እራሱን ዝቅ አድርጐ "ቦታውን ለሥራ ፈልጌዋለሁና በገንዘብ ሽጭልኝ" አላት። እርሷም እጅግ ከፍ ያለ ገንዘብ ጠየቀችው። ይኸውም አርባ ጊደር ላም መግዛት የሚችል ገንዘብ ነበር የጠየቀችው እርሱም ምንም ምን ሳይል ወርቁን ከፈላት። ቀይትም ገንዘቧን ተቀብላ ሔደችና እንደገና ተመልሳ "የምኖርበት ቦታ ስጠኝ" አለችው። እርሱም "ወደፊት ሌላ ቦታ እስክሰጥሽ በዚህ ቆይ" ብሎ ዛሬ ቆይታ የምትባለውን ቦታ ሰጣት ከዚህም የተነሳ ከግዜ ብዛት የቦታው መጠራያ ስም ቆይታ ተባለች። ይህች ቦታ የምትገኘው ከላሊበላ ከተማ በስተ ምሥራቅ በግምት ሁለት ኪ.ሜ ርቀት ላይ ነው። ለዚህ ነበር አባቶቻችን ንጉሥ ላሊበላ በአንጡራ ገንዘቡ የገዛውን ቦታ ስለሆነ በቦታው የሃይማኖት ሸቃጮች የሃይማኖት ሸቀጥ አያካሂዱበትም በማለት ለመስዋዕትነት የተዘጋጁት አሁንም ቢሆን ወደፊትም በዚህ ዙሪያ ላይ መናፍቅ ቦታ እንደሌለው ሊያውቅ ይገባል።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ ላሊበላ የህንፃ ሥራውን ለመጀመር ቦታው ጫካ ስለነበር በሰፊው የማጽዳት ዘመቻ ካካሄደ በኋላ የት ቦታ መጀመር እንዳለበትና የማንን ቤተ መቅደስ መጀመሪያ እንደሚሰራ እንደገና በሱባኤ ለፈጣሪው ጥያቄ አቀረበ። በጥያቄው መሠረትም ቅዱስ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ እንዳየው የወርቅ መሰላል ከሰማይ እሰከ ምድር የብርሃን አምድ ተተክሎ ዛሬ ቤተ ማርያም ካለችበት ቦታ አርፎ መላእክት ሲወጡበት ሲወርዱበት ቅዱስ ላሊበላ አየ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Dec, 17:38


25 ለምለም 40 ዮናስ የነፍስ ዋጋ ያድርግልን 🙏🙏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Dec, 17:33


ውድ ቤተሰቦች ለበረከት እንሳተፍ 🙏🙏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Dec, 17:33


✝️✝️✝️
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

💒💒💒
የደግነት በጎ አድራጎት መንፈሳዊ ማኅበር

✝️✝️✝️ (መጽሐፍ ምሳሌ16:24)ያማረ ቃል የማር ወለላ ነው ፤ለነፍስ ጣፋጭ ለአጥንትም ጤና ነው፡፡

ኑ ~ ለነፍሳችን እንጀራ እንሥራላት±💒
ከፍሬህም ሁሉ በኩራት ፤
         ጎተራህም እህልን ይሞላል
        መጥመቂያህም በወይን ጠጂ ሞልታ ትትረፈረፍለች ።" ምሳሌ 3፤9
 
ሐዋርያት 20፥35
“እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፦ ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር
(  1000532242685  )
ናትናኤል ታደለ እና ቴዎድሮስ አበራ
በማለት ማስገባት ይችላሉ🙏
ለ ጌታችን የ ልደት በዓል  ነዳያንን ለመርዳት  የተዘጋጀ ዕጣው👇 መጽሐፍ
ስለ ክርስቶስ ልደት በ (ቅዱስ አቡነ ሽኖዳ )
ዕጣው 100 መቶ ብር ሲሆን ለበረከት ተሳተፎ 🙏

1️⃣ ቴዲ
2️⃣
3⃣
4️⃣
5️⃣አዳሙ
6️⃣
7️⃣
8️⃣
9️⃣
🔟
1️⃣1️⃣
1️⃣2️⃣ ገብረ ማርያም ( Kalkidan)
1️⃣3️⃣
1️⃣4️⃣
1️⃣5️⃣
1️⃣6️⃣ፋሲካ
1️⃣7️⃣
1️⃣8️⃣
1️⃣9️⃣ አዳሙ
2️⃣0️⃣
2️⃣1️⃣ቴዲ
2️⃣2️⃣
2️⃣3️⃣
2️⃣4️⃣ወለተ ማርያም (kalkidan)
2️⃣5️⃣ለምለም
2️⃣6️⃣
2️⃣7️⃣
2️⃣8️⃣
2️⃣9️⃣
3️⃣0️⃣ፋሲካ
3️⃣1️⃣ ወለተ ህይወት
3️⃣2⃣
3️⃣3️⃣ሚዛን
3️⃣4️⃣
3️⃣5️⃣ሚዛን
3️⃣6️⃣
3️⃣7️⃣
3⃣8⃣
3⃣9⃣ወለተ ህይወት
4⃣0⃣ዮናስ (ለምለም)
4⃣1⃣
4⃣2⃣
4⃣3⃣
4⃣4⃣
4⃣5⃣
4⃣6⃣
4⃣7⃣
4⃣8⃣
4⃣9⃣
5⃣0⃣
5⃣1⃣
5⃣2⃣
5⃣3⃣
5⃣4⃣
5⃣5⃣ሳሙኤል (ናትናኤል )

1⃣0⃣0⃣
🔽🔽

2ኛ ቆሮ 9፥7
“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።”
"ቸርነትን፣ ትህትናን፣ የዋህነትን፣ ትዕግሥትን ልበሱ" ቆላስ 3፥12
ከዚህ በፊት የነበሩ የበረከት ስራዎች
👉 @kindnessvediophoto
ይቆየን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Dec, 20:40


#ታኅሣሥ_15

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም

ታኅሣሥ ዐስራ አምስት በዚህች እለት #ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘአርማንያ ዕረፍታቸው ነው፣ ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ #አቡነ_ኤዎስጣቴዎስ_ከፋሌ_ባህር ልደታቸው ነው፣ #የቅዱስ_አቡነ_ሉቃስ_ዘዓምድ ዕረፍታቸው ነው፣ የእኔ ቢጤ የነበሩትና ጽድቃቸውን ማንም ሳያውቅባቸው የኖሩት #የአባ_ቆራይ ዕረፍታቸው ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘአርማንያ

ታኅሣሥ ዐስራ አምስት በዚህች እለት የአርማንያ አገር ኤጲስቆጶስ አባ ጎርጎርዮስ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ይህንንም ቅዱስ የንጉሡን ትእዛዝ ስመተላለፋና ለአማልክት አልሠዋም ስላለ የአርማንያ ንጉሥ ድርጣድስ አሠቃይቶ ጥልቅ ወደ ሆነ ደረቅ ጒድጓድ ውስጥ ጨመረው በዚያ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረ። እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ነበር አንዲቷን አሮጊትም ሁል ጊዜ ምግቡን እነሰድታመጣለት አደረጋት ሕያው እንደሆነም የሚያውቅ የለም።

ንጉሥ ድርጣድስም ቅድስት አርሴማን ለማግባት ሽቶ ነበርና በእርሷ ምክንያት ደናግሎችን ገደላቸው። የእሊህ ደናግልም ሥጋቸው በተራራ ላይ እንደ ወደቀ ነበር ንጉሡም ስለ ገደላቸው ደናግል ይልቁንም ውበቷንና ደም ግባቷን እያሰበ ስለ ቅድስት አርሴማ አብዝቶ የሚያዝንና የሚጸጸት ሆነ።

ከዚህም በኋላ ወገኖቹ ለመኑት እንዲህም አሉት አውሬ ታድን ዘንድ በፈረስ ተቀመጥና ወደ ዱር እንውጣ የልብህም ኀዘን ይወገድልሃል። በዚያንም ጊዜ አውሬ ለማደን በፈረሱ ተቀምጦ ወደ ዱር ወጣ። የሚነክስ ሆነ ወገኖቹንም ነከሳቸው እግዚአብሔርም መልኩን ለውጦ እንደ እሪያ አደረገው ያገኘውን ሁሉ የሚነክሰ ሆነ። እንዲሁም ከቤተ መንግሥት ሰዎች በብዙዎቹ ላይ ሰይጣን አደረባቸው ታላቅ ድንጋጤም ሆነ ይህም ሁሉ የሆነ ስለ ቅዱሳት ደናግልና ስለ ቅድስት አርሴማ ነው።

የንጉሡ እኅት ግን "ጎርጎርዮስን ከጒድጓድ ካላስወጣችሁት ድኅነት የላችሁም" የሚላት ሰው በራእይ አየች ይህንንም ለወገኖቿ ነገረች እርሱ አስቀድሞ በጒድጓድ ውስጥ የሞተ ስለ መሳላቸው ደነገጡ። በዚያንም ጊዜ ወደ ጒድጓድ ሔዱ በሕይወት እንዳለም ያወቁ ዘንድ ወደ ጒድጓዱ ውስጥ ገመዶችን አወረዱና ገመዶቹን እንዲይዝ ወደርሱ ጮኹ እርሱም ገመዶችን ያዘ ስበው አወጡት አጥበውም ንጹሕ ልብስን አለበሱት በበቅሎም አስቀምጠው ወደ ቤተ መንግሥት አደረሱት። በዚያንም ጊዜ በሰማዕትነት ስለሞቱ ደናግል ሥጋ ጠየቀ እነርሱም የደናግሉ ሥጋቸው ወዳለበት መርተው አደረሱት የዱር አራዊትና አዕዋፍ ሳይበሏቸው በደኅና አገኛቸው ያማሩ ቦታዎችን አዘጋጅተው በውስጣቸው ያኖሩዋቸው ዘንድ አዘዘ እንዳዘዛቸውም አደረጉ።

ከዚህም በኋላ ንጉሡን ያድነው ዘንድ ሕዝቡ ለመኑት ንጉሡም ወዳለበት ዱር አደረሱት እርሱም "ከክፉ ሥራህ ትመለሳለህን? ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታምናለህን?" አለው። እሪያ የሆነውም ንጉሥ አዎን እንደሚል ራሱን ዘንበል አድርጎ አመለከተ በዚያንም ጊዜ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ጸለየ ከንጉሡም ላይ በእሪያ አምሳል ሰይጣንን አስወጣው። የንጉሡም አእምሮውና መልኩ እንደ ቀድሞው ተመለሰለት ነገር ግን ዳግመኛ እንዳይታበይ ከእግሩ ላይ የእሪያ ጥፍር አስቀረ ፈጣሪውም ተገዢ ይሆን ዘንድ ዳግመኛም የቤተ መንግሥት ሰዎችን ሁሉንም አዳናቸው ከላያቸውም አጋንትን አስወጥቶ ሰደዳቸው።

ከዚህም በኋላ የአርማንያን ሰዎች ሁሉንም ሰበሰባቸውና ሥርዓትን ሠራላቸው ስምንት ቀንም እንዲጾሙ አዘዛቸው እንዳዘዛቸውም አደረጉ የእግዚአብሔርንም ሕግ እያስተማራቸው ኖረ። ዳግመኛም ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መሆኑን አስተማራቸው ታላቆችም ታናናሾችም ትምህርቱን ተቀበሉት ለአርማንያ ሰዎች ሃይማኖትን የመቀበላቸው ምክንያት ይህ ነው።

ከዚህም በኋላ የክርስትና ጥምቀትን ያጠምቃቸው ዘንድ ቅዱስ ጎርጎርዮስን ለመኑት እርሱም "እኔ ካህን ስለአልሆንኩ አይገባኝም ነገር ግን የሚያጠምቃችሁን ካህን ይልክላችሁ ዘንድ ወደሮሜ ሊቀ ጳጳሳት መልክተኞችን ላኩ" አላቸው። በዚያንም ጊዜ ከርሱ ጋር ወደ ንጉሥ አኖሬዎስና ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ መልክተኞችን ልከው የአርማንያ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር እንደተመለሱ አስረዱአቸው ንጉሡም ሊቀ ጳጳሳቱም ሰምተው ደስ አላቸው ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ ለአርማንያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ይሆን ዘንድ ቅዱስ ጎርጎርዮስን ሾመው ወደ አርማንያን ንጉሥ ወደ ድርጣድስም በክብር ላከው።

ቅዱስ ጎርጎርዮስም ተሹሞ ወደ አርማንያ አገር በደረሰ ጊዜ በመምጣቱ ደስ ተሰኙበት እርሱም የአርማንያን ሰዎች ሁሉንም አጠመቃቸው በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያን ሠራላቸው ሃይማኖንትም ከአጸናቸውና መልካም ጉዞንም ከፈጸመ በኋላ ታኅሣሥ15 ቀን በሰላም በፍቅር ዐረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ኤዎስጣቴዎስ_ከፋሌ_ባህር

ዳግመኛም በዚህች ዕለት አጽፋቸውን እንደጀልባ ተጠቅመው የኢያሪኮን ባሕር የተሻገሩት ታላቁ ኢትዮጵያዊ ጻድቅ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር ልደታቸው ነው፡፡ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ አባታቸው ክርስቶስ ሞዐ ሲሆን እናታቸው ስነ ሕይወት ይባላሉ፡፡ ደጋግ የሆኑ ወላጆቻቸው በሃይማኖትና በምግባር ኮትኩተው አሳደጓቸው፡፡ በአደጉም ጊዜ ከአባ ዘካርያስ እጅ መነኮሱ፡፡ ታላላቅ ቅዱሳን እስኪያደንቋቸው ድረስ በጽኑ ተጋደሎ ሲኖሩ ጌታችን ከቅዱሳን መላእክቱ ጋር ተገልጦላቸው በንፍሐት መንፈስ ቅዱስን አሳደረባቸው፡፡ ‹‹ከእናትህ ማኅፀን የመረጥኩህ ወዳጄ ኤዎስጣቴዎስ ሆይ ለብዙዎች ወንጌልን ትሰብክ ዘንድ ከኢትዮጵያ እስከ አርማንያ ድረስ መምህር አደረግሁህ፡፡ አንተን የሰማ እኔን ሰማ፣ አንተንም ያልሰማ እኔን ያልሰማ ነው›› ካለቸው በኋላ ወደ ሰማይ በክብር ዐረገ፡፡

አባታችን ቅስናን ከተሸሾሙ በኋላ ወንጌልን መስበክ ጀመሩ፡፡ እነ አቡነ አብሳዲን ጨምሮ ብዙዎችንም አመንኩሰው ደቀ መዛሙርቶቻቸው አደረጓቸው፡፡ እጅግ አስገራሚ ተአምራትን በማድረግ ለብዙ ሕሙማን መድኃኒት ሆኗቸው፡፡ ልጆቻቸውን ሰብስበው ከመናፍቃን ጋር በፍጹም እንዳይቀላቀሉ በመምከር አቡነ አብሳዲን ሾመውላቸው ወደ ኢየሩሳሌም በመሄድ ቅዱሳት ቦታዎችን ተሳለሙ፡፡ በመንገዳቸውም የክርስቶስን ወንጌል እየሰበኩ ብዙዎችን ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሷቸው፡፡ ወደ አርማንያም ሄደው ወደ ኢያሪኮ ባሕር በደረሱ ጊዜ መርከበኞችን እንዲያሳፍሯቸው ቢለምኗቸው እምቢ አሏቸው፡፡ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ ግን አጽፋቸውን በባሕሩ ላይ ዘርግተው በስመ ሥላሴ አማትበው አጽፋቸውን እንደመርከብ አድርገው ልጆቻቸውን ይዘው ባሕሩን ተሻገሩ፡፡ ልጆቻቸውን ‹‹ልጆቼ በልባችሁ ቂምንና ሽንገላን እንዳታኖሩ ተጠበቁ፣ ለእኔ ግን ከእናንተ አንዱ እንደሚጠፋ ይመስላኛል›› አሏቸው፡፡ ይህንንም እንዳሉ ከመካከላቸው አንዱ የቂም በቀል መከማቻ ነበርና ወዲያው ሰጠመ፡፡

አባታችን አርማንያ ደርሰው ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር ቡራኬን ከተሰጣጡ በኋላ ማስተማር ጀመሩ፡፡ የአርማንያ ሰዎች ሁሉም በሃይማኖት አንድ እስኪሆኑ ድረስ ታላላቅ ተአምራትን እያደረጉ አስተምረው አጠመቋቸው፡፡ አባታችን ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታችን ተገልጦላቸው ታላቅ ቃልኪዳን ከሰጣቸው በኋላ መስከረም 18 ቀን ዐርፈው ሊቀ ጳጳሳቱና ካህናቱ በታላቅ ክብር ገንዘው በሰማዕቱ በቅዱስ መርምህናም ቤተ ክርስቲያን ቀብረዋቸዋል፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ሉቃስ_ዘዓምድ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Dec, 18:16


✝️✝️✝️
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

💒💒💒
የደግነት በጎ አድራጎት መንፈሳዊ ማኅበር

✝️✝️✝️ (መጽሐፍ ምሳሌ16:24)ያማረ ቃል የማር ወለላ ነው ፤ለነፍስ ጣፋጭ ለአጥንትም ጤና ነው፡፡

ኑ ~ ለነፍሳችን እንጀራ እንሥራላት±💒
ከፍሬህም ሁሉ በኩራት ፤
         ጎተራህም እህልን ይሞላል
        መጥመቂያህም በወይን ጠጂ ሞልታ ትትረፈረፍለች ።" ምሳሌ 3፤9
 
ሐዋርያት 20፥35
“እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፦ ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር
(  1000532242685  )
ናትናኤል ታደለ እና ቴዎድሮስ አበራ
በማለት ማስገባት ይችላሉ🙏
ለ ጌታችን የ ልደት በዓል  ነዳያንን ለመርዳት  የተዘጋጀ ዕጣው👇 መጽሐፍ
ስለ ክርስቶስ ልደት በ (ቅዱስ አቡነ ሽኖዳ )
ዕጣው 100 መቶ ብር ሲሆን ለበረከት ተሳተፎ 🙏

1️⃣ ቴዲ
2️⃣
3⃣
4️⃣
5️⃣አዳሙ
6️⃣
7️⃣
8️⃣
9️⃣
🔟
1️⃣1️⃣
1️⃣2️⃣ ገብረ ማርያም ( Kalkidan)
1️⃣3️⃣
1️⃣4️⃣
1️⃣5️⃣
1️⃣6️⃣ፋሲካ
1️⃣7️⃣
1️⃣8️⃣
1️⃣9️⃣ አዳሙ
2️⃣0️⃣
2️⃣1️⃣ቴዲ
2️⃣2️⃣
2️⃣3️⃣
2️⃣4️⃣ወለተ ማርያም (kalkidan)
2️⃣5️⃣
2️⃣6️⃣
2️⃣7️⃣
2️⃣8️⃣
2️⃣9️⃣
3️⃣0️⃣ፋሲካ
3️⃣1️⃣ ወለተ ህይወት
3️⃣2⃣
3️⃣3️⃣ሚዛን
3️⃣4️⃣
3️⃣5️⃣ሚዛን
3️⃣6️⃣
3️⃣7️⃣
3⃣8⃣
3⃣9⃣ወለተ ህይወት
4⃣0⃣
4⃣1⃣
4⃣2⃣
4⃣3⃣
4⃣4⃣
4⃣5⃣
4⃣6⃣
4⃣7⃣
4⃣8⃣
4⃣9⃣
5⃣0⃣
5⃣1⃣
5⃣2⃣
5⃣3⃣
5⃣4⃣
5⃣5⃣ሳሙኤል (ናትናኤል )

1⃣0⃣0⃣
🔽🔽

2ኛ ቆሮ 9፥7
“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።”
"ቸርነትን፣ ትህትናን፣ የዋህነትን፣ ትዕግሥትን ልበሱ" ቆላስ 3፥12
ከዚህ በፊት የነበሩ የበረከት ስራዎች
👉 @kindnessvediophoto
ይቆየን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Dec, 18:15


የታል የታል እልልታ
አቡነ አረጋዊን ያላቹሁ
የታለ እልልታ 👏👏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Dec, 18:06


እልልል ከአስተባባሪዎች ወለተ ማርያም ቃልኪዳን -24 እና 12 በ ገብረማርያም 👏👏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Dec, 18:02


✝️✝️✝️
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

💒💒💒
የደግነት በጎ አድራጎት መንፈሳዊ ማኅበር

✝️✝️✝️ (መጽሐፍ ምሳሌ16:24)ያማረ ቃል የማር ወለላ ነው ፤ለነፍስ ጣፋጭ ለአጥንትም ጤና ነው፡፡

ኑ ~ ለነፍሳችን እንጀራ እንሥራላት±💒
ከፍሬህም ሁሉ በኩራት ፤
         ጎተራህም እህልን ይሞላል
        መጥመቂያህም በወይን ጠጂ ሞልታ ትትረፈረፍለች ።" ምሳሌ 3፤9
 
ሐዋርያት 20፥35
“እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፦ ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር
(  1000532242685  )
ናትናኤል ታደለ እና ቴዎድሮስ አበራ
በማለት ማስገባት ይችላሉ🙏
ለ ጌታችን የ ልደት በዓል  ነዳያንን ለመርዳት  የተዘጋጀ ዕጣው👇 መጽሐፍ
ስለ ክርስቶስ ልደት በ (ቅዱስ አቡነ ሽኖዳ )
ዕጣው 100 መቶ ብር ሲሆን ለበረከት ተሳተፎ 🙏

1️⃣ ቴዲ
2️⃣
3⃣
4️⃣
5️⃣አዳሙ
6️⃣
7️⃣
8️⃣
9️⃣
🔟
1️⃣1️⃣
1️⃣2️⃣ ገብረ ማርያም ( Kalkidan)
1️⃣3️⃣
1️⃣4️⃣
1️⃣5️⃣
1️⃣6️⃣ፋሲካ
1️⃣7️⃣
1️⃣8️⃣
1️⃣9️⃣ አዳሙ
2️⃣0️⃣
2️⃣1️⃣ቴዲ
2️⃣2️⃣
2️⃣3️⃣
2️⃣4️⃣ወለተ ማርያም (kalkidan)
2️⃣5️⃣
2️⃣6️⃣
2️⃣7️⃣
2️⃣8️⃣
2️⃣9️⃣
3️⃣0️⃣ፋሲካ
3️⃣1️⃣ ወለተ ህይወት
3️⃣2⃣
3️⃣3️⃣ሚዛን
3️⃣4️⃣
3️⃣5️⃣ሚዛን
3️⃣6️⃣
3️⃣7️⃣
3⃣8⃣
3⃣9⃣ወለተ ህይወት
4⃣0⃣
4⃣1⃣
4⃣2⃣
4⃣3⃣
4⃣4⃣
4⃣5⃣
4⃣6⃣
4⃣7⃣
4⃣8⃣
4⃣9⃣
5⃣0⃣
5⃣1⃣
5⃣2⃣
5⃣3⃣
5⃣4⃣
5⃣5⃣ሳሙኤል (ናትናኤል )

1⃣0⃣0⃣
🔽🔽

2ኛ ቆሮ 9፥7
“እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ በኀዘን ወይም በግድ አይደለም።”
"ቸርነትን፣ ትህትናን፣ የዋህነትን፣ ትዕግሥትን ልበሱ" ቆላስ 3፥12
ከዚህ በፊት የነበሩ የበረከት ስራዎች
👉 @kindnessvediophoto
ይቆየን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Dec, 18:02


ይህ ከላይ የምታዩት መጽሐፍ
ስለ ክርስቶስ ልደት በ አቡነ ሺኖዳ የተጻፈ ሲሆን ለ ገና ለነዲያን ማስፈሰጊያ የሚሆን ገቢ ማሰባሰቢያ በዕጣ መልክ የተዘጋጀ ነው ::
ለበረከት ተሳተፎ ዕጣው 100 መቶ ብር ነው 🙏🙏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

09 Dec, 13:02


✟ እንዳልዘምር የሚከለክለኝ ምንድን ነው?


የ 2017 የአእላፋት ዝማሬ መዝሙር ተለቀቀ ሙሉ
መዝሙሮችን ለማግኘት በጃን ያሬድ የቴሌግራም
ሚዲያ ላይ ያገኛሉ።


https://t.me/+1rCQMEj6K2kzM2E8

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

09 Dec, 08:48


!!በቅዳሴ ጊዜ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ጥንቃቄዎች!!



ዲ/ን ዘላለም ታዬ💖


በቸር ዋሉ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

08 Dec, 20:17


#ኅዳር_30

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ኅዳር ሠላሳ በዚህች ቀን ጻድቁ #ንጉሥ_አፄ_ገብረ_መስቀል ዕረፍቱ ነው፣ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አባት_አካክዮስ አረፈ፣ #የቅዱሳን_ቆዝሞስና_ድምያኖስ ቤተ ክርስቲያናቸው የከበረችበት ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አፄ_ገብረ_መስቀል_ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)

ኅዳር ሠላሳ በዚህች ቀን ጻድቁ ንጉሥ አፄ ገብረ መስቀል ዕረፍቱ ነው።

ዐፄ ካሌብ የናግራንን ሰማዕታት ደም ተበቅሎ በድል ከተመለሰ በኋላ በአቡነ ጰንጠሌዎን እጅ መንኩሶ ገዳም ከገባ በኋላ ልጁ ገብረ መስቀል ነገሠ፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀል በእውነትና በቅንነት ከነገሠ በኋላ አመራሩ ከአህጉሪቷ ጽንፍ እስከ ጽንፍ ደረሰ፡፡ በዘመኑም ሁሉ መንግሥቱን የሚቃወም አልተነሣም፤ እርሱም ቤተ ክርስቲያንን ከመሥራት በቀር ወደ ጦርነት የሄደበት ጊዜ የለም፡፡ መንግሥቱንም ይባርክለት ዘንድ ሠራዊቱን ይዞ ወደ አባታችን ወደ አቡነ አረጋዊ ዘንድ ደብረ ዳሞ ሄደና በፊቱ ሰግዶ ‹‹አባቴ ሆይ! እኔን ባሪያህን፣ መንግሥቴንና ሕዝቤን ሠራዊቴንም ሁሉ ባርክ›› እያለ አጥብቆ ማለደው፡፡ አባታችን አረጋዊም ‹‹የአባቶችህን የዳዊትንና የሰሎሞንን መንግሥት የባረከ፣ የአባትህን የካሌብንም መንግሥት የባረከ እግዚአብሔር የአንተንም መንግሥት ይባርክ…›› ብለው ባረኩት፡፡ ከዚህም በኋላ ንጉሥ ዐፀ ገብረ መስቀል አቡነ አረጋዊን የት ቦታ ላይ ቤተክርስቲያን እንደሚሠራ ጠይቋቸው ካሳዩት በኋላ ሲሠራ ሁለት ዓመት የፈጀበት ግሩም ቤተክርስቲያን ሠራላቸውና 12 የወርቅና የብር መስቀሎችን ጨምሮ ብዙ ንዋያተ ቅድሳቶችንና ሥጦታዎችን ሰጣቸው፡፡ ጳጳስም አስመጥቶ አስባረካትና ከማኅበረ በኩር ያመጣውን በወርቅ በብር የተለበጠች የእመቤታችንን ታቦት በውስጧ አስገባ፡፡ ጳጳሱና ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀልም አቡነ አረጋዊን ‹‹ቀድሰህ አቁርበን›› ብለውት ይቀድስ ዘንድ በገባ ጊዜ መላእክት ሙቀት ያልተለየው ኅብስትና ወይኑን በጽዋ ለቅዳሴው የሚያስፈልገውንም ሁሉ ከሰማይ አወረዱለትና ቀድሶ ሲያበቃ ሁሉንም አቆረባቸው፡፡

ከዚህም በኋላ ንጉሡ ዐፄ ገብረ መስቀል ከተራራው ጫፍ በሚወርድበት ጊዜ አባታችንን ‹‹ይህን የተራራውን መውጫ መሰላል ላፍርሰው ወይስ ልተወው?›› አለው፡፡ አባታችንም ‹‹ለልጅ ልጅ መታሰቢያ እንዲሆን ይህን ድንቅ ሥራ እያየ በፍጥረቱ ሁሉ አንደበት እግዚአብሔር ይመሰገን ዘንድ የደረጃውን መሰላል አፍርሰው፣ ነገር ግን ስለዘንዶው ጅራት ፋንታ ገመድ አብጅ›› አለው፡፡ ንጉሡም እንደታዘዘው የደረጃውን መሰላል አፈረሰውና ወደ ቤተ መንግሥቱ ተመለሰ፡፡ ጻድቁ ንጉሥ በዐፄ ገብረ መስቀል ካበረከተልን ትልቅ ውለታው ውስጥ አንዱ ዛሬ በዩኔስኮ የተመዘገበውን የመስቀል በዓልን በአደባባይ እንዲከበር ያደረገ መሆኑ ነው፡፡ በዘመኑም ካህናቱ ሕዝቡ ሁሉ አደይ አበባ ይዘው ወደ አደባባይ በመውጣት በያሬዳዊ ዝማሬ የመስቀልን በዓል ያከብሩ ነበር፡፡

የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ብርሃኗ የሆነ ነገር ግን እርሷ እንደሚገባው መጠን ያላከበረችው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በዚህ ጻድቅ ንጉሥ በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት የነበረ ነው፡፡ አብረውም ብዙ ታሪኮችን ፈጽመዋል፡፡ ገዳማትን ላይ በመዟዟር ቅዱስ ያሬድ ዜማን ሲያስተምር ንጉሡ ደግሞ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ ያስፋፉና ቋሚ መተዳደሪያ ይሰጡ ገዳማቱን ያጠናክሩ ነበር፡፡ አቡነ አረጋዊ ደግሞ አብረው ምኩስናን ያስፋፉ ነበር፡፡ ሦስቱም ይህን ተግባራዊ እንዳደረጉ ለማሳያ ይሆን ይሆን ዘንድ ቅዱስ ያሬድ 3 ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት ያስተማረባትንና ዛሬም ድረስ ማስመስከሪያ የሆነችውን እጅግ ጥንታዊቷን ዙር አባ ጽርዓ አርያም አቡነ አረጋዊ ገዳምን እንደምሳሌ ማየት እንችላለን፡፡ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ያሬድ በዘንዶ ታዝለው ዓምባው ላይ ከወጡ በኋላ ለንጉሡ ለዐፄ ገብረ መስቀል ደግሞ ተራራውን ባርከው ከፍለው መንገድ አበጅተውላቸው ወደ ዓምባው ወጥተው ሦስቱም በዚያ በጋራ ኖረው ብዙ መንፈሳዊ ሥራን ሠርተዋል፡፡

ጻድቁ ንጉሥ ዐፄ ገብረ መስቀል ከተስዓቱ ቅዱሳን ጋር ሆኖ ብዙ መንፈሳዊ ሥራን ሠርቷል፡፡ ሌላው በዐፄ ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት ከነበሩት ቅዱሳት አንስት ውስጥ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዋነኛዋ ናት፡፡ ይኽችውም ቅድስት ከልጅነቷ ጀምራ በምግባር በሃይማኖት፣ በተጋድሎ በትሩፋት ያጌጠች ናትና ንጉሠ ነገሥቱ ዐፄ ገብረ መስቀል በሁለመናዋ የተመሰገነች መሆኗንና ዝናዋን ስለሰማ ‹‹በጸሎትሽ አስቢኝ›› በማለት ከአገልጋዮቹ ውስጥ እርሷን እንዲያገለግሏት 174 አገልጋዮችን ልኮላታል፡፡ ለነገሥታት ሚስቶች የሚደረገውን በሐርና በወርቅ የተሠሩ ልብሶችና ጫማ ልኮላታል፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀል በጽድቅ ሕይወት እየተመላለሱ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን የዋሉት ውለታ እጅግ ብዙ ነው፡፡ ገርዓልታ አካባቢ ከዱጉም ሥላሴ በእግር የ2 ሰዓት መንገድ ርቀት ላይ የቅዱስ ዐፄ ገብረ መስቀል አስደናቂ ፍልፍል ቤተ መቅደስ ይገኛል፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባት_አካክዮስ

በዚህች ቀን የቊስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት አካክዮስ አረፈ።

ይህም ቅዱስ ቸር የሆነ ምሁር ነው አምላክ ያጻፋቸውንም መጻሕፍት ቃላቸውን አሳምሮ የሚተረጉም አዋቂ ነው በቁስጥንጥንያ ቤተ ክርስቲያንም ቅስና ተሹሞ ነበር ። በኬልቄዶንም ስብሰባ በሆነ ጊዜ ይህ አባት በጉባኤው ውስጥ በሆነው ሁሉ ደስ አላለውም ስለ እውቀቱም እንዲመጣ በፈለጉት ጊዜ እርሱ አሞኛል ብሎ ስለራሱ ምክንያት ሰጠ።

በእስክንድርያ አገር ሊቀ ጳጳሳት በቅዱስ ዲዮስቆሮስ ላይ ስለ ደረሰበት ሥቃይ በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ሃይማኖታቸው የቀና እንደሆነ በሚያውቃቸው ባልንጀሮቹ በሆኑ በወዳጆቹ በወታደር አለቆችና በመኰንኖች ፊት የአንድነት ጉባኤያቸውን ረገመ ከእሊህም ክፉዎች ከጉባኤያቸው አንድ ያላደረገኝ እግዚአብሔርን አመሰግነዋለሁ አለ ።

የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳት እንጣልዮስም በአረፈ ጊዜ ሃይማኖቱ የቀና እንደ ሆነ ስለ አወቁ የአገሩ ሊቃውንትና መኳንንት ይህን አባት አካክዮስን መረጡት። እርሱ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሆነው መጣላትና መለያየትን ያስወግዳል በማለት ተስፋ አድርገው በቁስጥንጥንያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት።

በተሾመ ጊዜም ከብቻው እግዚአብሔር በቀር ማንም ሊአስወግደው የማይችል የጥልና የመለያየት የማይድን በሽታ አገኘ በልቡም አስቦ መጀመሪያ ራሴን አድን ዘንድ አይሻለኝምን አለ የቅዱሳን አባቶችን የቄርሎስንና የዲዮስቆሮስን የቀናች ሃይማኖት የተማረና በእርሷ የጸና መሆኑን እየታመነለት ከዚህም በማስከተል በክህነት ሥራ በመሳተፍ ይቀበለው ዘንድ ወደ እስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ሦስተኛው ጴጥሮስ መልእክትን ላከ።

አባ ጴጥሮስም መልእክቱን በአነበበ ጊዜ ደስ ብሎት ታላቅ ክብርን አከበረው ያቺንም መልእክት በጉባኤ ፊት አስነባባት ከዚህም በኋላ አባ ጴጥሮስ ለመልእክቱ መልስ ጽፎ ከሦስት ኤጲስቆጶሳት ጋር ወደ አካክዮስ ላከ እነርሱም ወደ ቁስጥንጥንያ ከአባ አካክዮስ ዘንድ በደረሱ ጊዜ የአባ ጴጥሮስን ደብዳቤ ሰጡት እርሱም ሃይማኖታቸው በቀና በወዳጆቹና በሀገሩ መኳንንት ፊት አነበባት።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

08 Dec, 09:16


#ድንቅ ትምህርት!!በማስተዋል እንከታተል!!




መ/ር ብርሃኑ አድማስ💖




መልካም ዕለት ሰንበት💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

08 Dec, 08:57


ተወዳጆች ሆይ

ንስኃን ምንጣበት ጊዜ አለ

አንደኛው ፦ልብ ሲደንድን ነው
ሁለተኛው :- ከሞት በኋላ ንስኃ የለም

ልብ ሲደነድን ማለት ምን ማለት ነው ?

ሰው እንዲህ ያደርጋል

ምን?

ሰው ኃጢአትን ከሰው ያየዋል

ያይና ያደንቀዋል
ያደንቅና ይመኘዋል
ይመኝና ያደርገዋል
ያደርግና ይደጋግመዋል
ይደጋግግምና ይለምደዋል
ይለምድና ጠባይ ያደርገዋል
ጠባይ ካደረገው በኋላ አልለቀው ይላል
አለቀው ሲል ልቡ ይደነድናል
ልቡ ሲደነድን ምን ይሆናል ከዚያ በኋላ

"ዘይፈልጥ ፀጋመ ወየማነ" ይሆናል ማለት ነው ።

ቀኝ እና ግራቸውን የማይለዩ የነነዌ ሰዎች

የት ናቸው ? መልሱ ለሁላችን ይሁን

ኃጢዓትን ከሚሰሩ ሰዎች ምን ህብረት አለን።
ፈጣሪ በነሱ መንገድ ከመሄድ ይጠብቀን🙏


ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን🙏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

07 Dec, 20:54


††† እንኳን ለአእላፍ ሰማዕታት: ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱሳን ሰማዕታት †††

††† ቤተ ክርስቲያን ዛሬ (ኅዳር 29) የሁሉንም ሰማዕታት በዓል ታከብራለች:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ (ቅዱሱ ሊቅ) በመጽሐፈ ሰዓታት ሰማዕታትን:-
"መስተጋድላን ከዋክብት ብሩሃን::
ማኅትዊሃ ለቤተ ክርስቲያን::" ይላቸዋል::

በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የሮም መንግስት ዓለምን የሚያስተዳድረው በሁለት ከተሞች: ማለትም በራሷ በሮምና በአንጾኪያ ነበር:: የወቅቱ ንጉሥ ኑማርያኖስ ሲሆን የቤተ መንግስቱ ልዑላንና የጦር አለቆች ቅዱሳኑ:- *ፋሲለደስ: *ገላውዴዎስ: *ፊቅጦር: *መቃርስ: *አባዲር: *ቴዎድሮስ (ሦስቱም): *አውሳብዮስ: *ዮስጦስ: *አቦሊ: ሌሎቹም ነበሩ::

ሴቶቹ ደግሞ ቅዱሳቱ:- *ማርታ: *ሶፍያ: *ኢራኢ: *ታኡክልያ: ሌሎቹም ነበሩ:: ለእነዚህ ሁሉ የበላይ ደግሞ ቅዱስ ፋሲለደስ ነበር:: ወቅቱ ከፋርስ: ከቁዝና ከበርበር ጦርነት የሚበዛበት ነበርና ባጋጣሚ ንጉሡ ኑማርያኖስ በሰልፍ መካከል ተመትቶ ወደቀ (ሞተ)::

የሮም መንግስትም ባዶ ሆነች:: ዙፋኑን መያዝ ለቅዱስ ፋሲለደስም ሆነ ለሌሎቹ ቅዱሳን ቀላል ነበር:: ግን እነሱ ዝም ብለው ጠላትን ለመዋጋት ወጡ::

በዘመኑ ደግሞ በግብጽ የፍየል እረኛ የነበረና ከልጅነቱ ሰይጣን የሚያናግረው አንድ አግሪጳዳ የሚሉት ጉልበተኛ ሰው ነበር:: ንጉሡ ከወለዳቸው ልጆች ሁለቱ ሴቶች ክፉዎች ነበሩና ትንሿ አግሪጳዳን ማንም በሌለበት አንግሣ ጠበቀቻቸው:: ስሙንም ዲዮቅልጢያኖስ አለችው::

በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ከሰይጣን ቀጥሎ እንደዚህ የከፋ ስም የለም:: የዓለም ክርስቲያኖችን የጨፈጨፈ ሰው ነው:: ትልቋ ደግሞ የትንሿን አይታ መክስምያኖስ የሚባል አውሬ አግብታ አነገሠችው:: ዓለምም በእነዚህ ጨካኝ ሰዎች እጅ ወደቀች::

ሠራዊቱ ሁሉ በሚሊየን ይቆጠራሉ:: የተደረገውን ሲያዩ ተበሳጩ:: ይህንን የተመለከተው ቅዱሱ ፋሲለደስ ግን ልዑላኑንና አለቆችን ሰብስቦ:- "ይህ ዓለም ከነ ክብሩ ጠፊ ነው:: ስለዚህ የተሻለውን የክርስቶስን መንግስት እንምረጥ" አላቸው:: ሁሉም እንደ አንድ ልብ መካሪ ደስ ተሰኝተው ምድራዊ ክብራቸውን ሊተው ወሰኑ::

ቀጥለውም በአንድ ቤት ተሰብስበው ይጾሙ: ይጸልዩ ገቡ:: ወደ ውጪ የሚወጡት ለምጽዋት ብቻ ነበር:: ከሃዲውም ይህንን ሲያይ የልብ ልብ ተሰማው:: ከድሮ ያሰበውንና ክርስቲያኖችን የማጥፋቱን እቅድ ሊፈጽም ምክንያት አገኘ::

አባ አጋግዮስ በሚባል መነኩሴ ምክንያት "አብያተ ክርስቲያናት ይትዐጸዋ: አብያተ ጣዖታት ይትረኀዋ - ቤተ ክርስቲያኖች ይዘጉ: ቤተ ጣዖቶችም ይከፈቱ" አለ:: አጵሎን: አርዳሚስ የሚባሉ ጣዖቶችንም አቆመ::

በዚህ አዋጅ ምክንያትም የክርስቲያኖች ሰቆቃ ጀመረ::
*ምድር በደም ታጠበች::
*ቅዱሳኑ ቀባሪ አጡ::
*እኩሉ ተገደለ:: እኩሉ ተቃጠለ:: እኩሉ ታሠረ:: እኩሉም ተሰደደ::

የቤተ ክርስቲያን ታሪክ የተጻፈው በብራናና በብዕር አይደለም:: ይልቁኑ እንደ ቀለም የሰማዕታት ደማቸው: እንደ ብዕር አጥንታቸው: ቆዳቸው እንደ ብራና ሆኖ ተጽፏል እንጂ:: ሰማዕታት ለሃይማኖታቸው የከፈሉት ዋጋ እጅግ ታላቅ ነው::

ስለዚህም "ተጋዳዮች: የሚያበሩ ኮከቦች: የቤተ ክርስቲያን ሻማዎች" ተብለው: እነሱ እየቀለጡ አብርተዋል:: ሰማዕትነት በብሉይ ኪዳን የጀመረና እስከ ዳግም ምጽዐተ ክርስቶስም የሚቀጥል ቢሆንም "ዘመነ ሰማዕታት" የሚባለው ከ150 እስከ 312 ዓ/ም ድረስ ያለው ዘመን ነው::

በተለይ ግን ከ270ዎቹ እስከ 312 ዓ/ም ድረስ ያሉ ዓመታት እጅግ የከፉ ነበሩና: የአርባ ሰባት ሚሊየን (47,000,000) ክርስቲያኖች ደም በምድር ላይ ፈሷል:: የሰማዕታት ምሥጢራቸው ቃለ ወንጌል: የጌታ ስብከትና ሕይወት እንጂ ሌላ አይደለም:: (ማቴ. 10:16, ማር. 13:9, ሉቃ. 12:4, ዮሐ. 16:1, ሮሜ. 8:35, ራዕይ. 2:9)

የቅዱሳን ሰማዕታት መነሻቸው ቅዱስ እስጢፋኖስ ሲሆን ፍጻሜአቸው ደግሞ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ጳጳሳት ነው::

††† ቅዱስ ጴጥሮስ ሰማዕት †††

††† ይህ ቅዱስ የሚታወቀው "ተፍጻሜተ ሰማዕት (የሰማዕታት መጨረሻ)" በሚለው ስሙ ነው::
ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-
የቅዱሱ ሃገረ ሙላዱ ግብጽ ናት:: ዘመኑም 3ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: ወላጆቹ ካህን ቴዎድሮስና ቡርክት ሶፍያ ልጅ አጥተው ሐምሌ 5 ቀን ወደ ፈጣሪ ቢማጸኑ በራዕይ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ተገልጠው ብሥራትን ለሶፍያ ነገሯት:: በወለደችው ጊዜም በራዕዩ መሠረት "ጴጥሮስ" አለችው::

ሰባት ዓመት በሆነው ጊዜም ለቤተ እግዚአብሔር ሰጥተው በሊቀ ጳጳሳቱ ቅዱስ ቴዎናስ እጅ አደገና በወጣትነቱ ሊቅ: ጥዑመ ቃልና በጐ ሰው ሆነ:: ዲቁናና ቅስናን ተሹሞ ሲያገለግል ቅዱስ ቴዎናስ በማረፉ ቅዱስ ጴጥሮስን የግብጽ 17ኛ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት::

ዘመኑ ደግሞ እጅግ ጭንቅ ነበር:: ክርስቲያኖች በተገኙበት ስለሚገደሉ: አብያተ ክርስቲያናትም ስለ ተቃጠሉ የቅዱሱ መከራ የበዛ ነበር:: ለ14 ዓመታት በፍጹም ትጋት ከመንጋው ጋር ተጨነቀ::

አርዮስን (ተማሪው ነበር) አውግዞ ለየው:: ከጌታ ጋርም ብዙ ጊዜ ተነጋገረ:: ብዙ ተአምራትንም ሠራ:: በዚህ ሁሉ ጊዜ አንድም ቀን በመንበረ ጵጵስናው ላይ አልተቀመጠም:: በኋላ ግን ጨካኙ ንጉሥ እንዲገደል አዘዘ::

ሕዝቡ "ከእሱ በፊት እኛን ግደሉን" በማለታቸው ሁከት እንዳይነሳ ቅዱስ ጴጥሮስ ተደብቆ ሔደና በፈቃዱ ለወታደሮች ተሰጠ:: በዚያች ሌሊትም የእርሱ ደም የግፍ ማብቂያ እንዲሆን እያለቀሰ ጮኸ:: ከሰማይም "አሜን! ይሁን!" የሚል ቃል መጣ:: ያን ጊዜ የእርሱ አንገት ተሰየፈ:: ዘመነ ሰማዕታትም አለፈ::

††† ቅዱስ ቀሌምንጦስ ዘሮም †††

††† የዚህ ቅዱስ ሐዋርያ ስሙ እንደ ምን ያምር! እንደ ምንስ ይከብር! ለቤተ ክርስቲያን ትልቁ ድልድዩዋ ነውና:: ቅዱስ ቀሌምንጦስ የቅዱስ ቀውስጦስና የቅድስት አክሮስያ ልጅ ሲሆን ወንድምም ነበረው::

አባትና እናቱም የሮም መሳፍንት: በስብከተ ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት ያመኑ: ገንዘባቸውን በምጽዋት የጨረሱ የመጀመሪያዎቹ የሮም ክርስቲያኖች ናቸው:: ልጆቻቸው (ቀሌምንጦስና ወንድሙ) በመርዝ ቢሞቱባቸው በአምላከ ጴጥሮስ ተማጽነው ተነስተውላቸዋል::

አንድ ጊዜ ቀውስጦስ በሌለበት አንድ ሰው አክሮስያን ስላስቸገራት ልጆቿን ይዛ ተሰዳለች:: በመንገድም መርከባቸው ተሰብሮ ቅዱስ ቀሌምንጦስ በስባሪው ግብጽ ደርሷል:: በዚያም ቅዱስ ጴጥሮስን አግኝቶት የሊቀ ሐዋርያት ደቀ መዝሙሩ ሆኗል::

ቅዱስ ጴጥሮስንም ተከትሎ ለአገልግሎት ብዙ አሕጉራትን ዙሯል:: ብዙ ምሥጢራትንም ተካፍሏል:: የቅዱሳን ሐዋርያትን ዜናም ከቅዱስ ሉቃስ (ግብረ ሐዋርያት) ቀጥሎ የጻፈ እርሱ ነው::

ቅዱሳን ሐዋርያት ሙሉ ቀኖናቸውን ለቅዱስ ቀሌምንጦስ ሲሰጡት ቅዱስ ጴጥሮስ ደግሞ ሰብአ ሰገል ለክርስቶስ ያመጡትን ወርቅ: እጣን: ከርቤውን አስረክቦታል:: በተለይ ሁሉም ሐዋርያት ባረፉ ጊዜ እርሱ ቤተ ክርስቲያንን ተረከበ:: በሮም ሁለተኛው ፓትርያርክ ሆነ::

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

07 Dec, 20:54


በጊዜው መጽሐፈ ቅዳሴ ባለ መደራጀቱ ሥጋውን ደሙን ሲፈትቱ ፈጣሪ እንዳመለከታቸው ይጸልዩ ነበር:: ቅዱሱ ግን የጌታንና የሐዋርያትን ቅዳሴ ዛሬ በምናየው መንገድ አደራጅቶ ጽፎታል:: በስሙ የሚጠራና "ቀሌምንጦስ" የሚባል መጽሐፉም (8 ክፍሎች አሉት) ከ81ዱ (አሥራው) መጻሕፍት ተቆጥሮለታል::

ቅዱሱ ሐዋርያ እንዲህ ሲመላለስ ኖሮ በ2ኛው መቶ ክ/ዘመን መጀመሪያ አካባቢ በጠራብሎስ እጅ ወደቀ:: ንጉሡም "ክርስትናን አስተምረሃል" በሚል ብዙ አሰቃይቶ: ከትልቅ ድንጋይ ጋር አስሮ ባሕር ውስጥ አስጥሞታል:: በዚህም ዐርፏል::

ሁሌ ግን በዓመት በዓመት ባሕሩ እየተከፈለላቸው: ምዕመናን እየገቡ ከቅዱስ አካሉ ይባረካሉ:: ቅዱሱን ብዙ ጊዜ "ቀሌምንጦስ ዘሮም" የምንለው "ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ" የሚባል መናፍቅ ስላለ ከእርሱ ለመለየት ነው::
የቅዱሱ ክብር በእውነት ታላቅ ነው!

††† አምላከ ሐዋርያት ወሰማዕት በመከራቸው ከመከራ ይሰውረን:: በረከታቸውንም ያብዛልን::

††† ኅዳር 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱሳን ሰማዕታተ ክርስቶስ (ሁሉም)
2.ቅዱስ ጴጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
3.ቅዱስ ቀሌምንጦስ ሐዋርያ (ዘሮም)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት
2.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ
3.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮጵያዊት
4.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ
5.ቅድስት አርሴማ ድንግል

††† "አቤቱ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ::
የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ::
ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት::
የባሪያዎችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች አደረጉ::
የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት::
ደማቸውንም በኢየሩሳሌም ዙሪያ እንደ ውኃ አፈሰሱ::
የሚቀብራቸውም አጡ::" †††
(መዝ. ፸፰፥፩)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

07 Dec, 19:34


💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕

[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛

🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

07 Dec, 18:16


በግምት ከሌሊቱ 8 ሰአት ገደማ ነው ሶስት ጓደኛማቾች እንደ ለመደባቸው ቅዳሜን ወጥተው ክለብ ለክለብ እየተዝናኑ ሰአታትን አስቆጥረዋል እንደ አጋጣሚ ሆኖ እጃቸው ላይ ያለውን ብር የትራንስፖርት እንኳን ሳያስከሩ መጨረሳቸውን ያስተዋሉት ከረፈደ ነበር ያው የሁልጊዜ ቤታችን ስለሆነ ዱቤ ይሠጡናል ብለው አስተናጋጁን ይጠሩትና የተፈጠረውን ያስረዱታል እንደ አጋጣሚ ሆኖ ሞባይል ባንኪንግ የማይጠቀሙበትን ተቀያሪ ስልካቸውን እንደያዙና እጃቸው ላይ በዚህ ሰአት ምንም ብር እንደሌላቸው ይነግሩታል እሱም ወደ ማናጀሩ መሄድ ሲጀምር.....see more

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Dec, 07:08


መንፈሳዊነት ምንድን ነው ?


፩. መንፈሳዊነት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ኅብረትና አንድነት ነው፡፡

፪. መንፈሳዊነት ስሜትን፣አእምሮንና መንፈስን ሲገዛ ነው፡፡

፫. መንፈሳዊነት ጥረት፣ተጋድሎ፣ ውጣ ውረድ ነው

፬. መንፈሳዊነት ጊዜና ቦታ የማይወስነው ነው፡፡

፭. መንፈሳዊነት የኑሮ ሁኔታ የማይወስነው ነው፡፡

በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ💖




እናንብብ መልካም ቀን🌹

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Dec, 03:22


ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አደራችሁ


እንኳን ለቸሩ መድኃኒዓለም አደረሳችሁ አደረሰን🌹

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Dec, 20:23


በሃይማኖቱም ከንጉሡ ጋር እንደተስማማ የተቀደሱ እናቱ ሚስቱና እኅቱ በሰሙ ጊዜ እንዲህ ብለው ጽፈው ወደርሱ ላኩ የቀናች የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ትተህ የፍጡራንን ጠባይ ለምን ተከተልክ እሊህም ፀሐይ ጨረቃ ከዋክብት እሳት ናቸው ዕወቅ ከዛሬ ጀምሮ በንጉሥ ሃይማኖት ከኖርክ እኛ ከአንተ የተለየን ነን።

የመልእክታቸውንም ጽሑፍ በአነበበ ጊዜ መሪር ልቅሶን አለቀሰ በዚህም የጥፋት ምክር ጸንቼ ብኖር ከቤተ ሰቦቼና ከወገኖቼ የተለየሁ መሆኔ ነው ። ደግሞስ በጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ፊት እንዴት እቆማለሁ አለ ከዚህም በኋላ የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍቶች ማንበብ ጀመረ የንጉሡን አገልግሎትም ተወ ለንጉሡም ወዳጅህ ያዕቆብ እነሆ አገልግሎትህን አማልክቶችህንም ማምለክ ተወ ብለው ነገሩት።

ንጉሡም ልኮ ወደርሱ አስቀርቦ አገልግሎትህን ለምን ተውክ አለው ቅዱስ ያዕቆብም እንዲህ አለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከበረ ወንጌል በሰው ፊት ያመነብኝን ሁሉ እኔም በሰማያዊ አባቴ ፊት አምነዋለሁ በሰው ፊት የካደኝንም በአባቴ ፊትና በመላእክት ፊት እክደዋለሁ ብሏልና ስለዚህ አገልግሎትህን ፍቅርህን አማልክቶችህንም ማምለክ ትቼ ሰማይና ምድርን ፀሐይን ጨረቃን ከዋክብትን የሚታየውንና የማይታየውን ለፈጠረ ለሕያው እግዚአብሔር ልጅ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ የምሰግድ ሆንኩ።

ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ ደሙ እንደ ውኃ በዝቶ እስቲፈስ ታላቅ ግርፋትን እንዲገርፉት አዘዘ እርሱ ግን ከበጎ ምክሩ አልተመለሰም ዳግመኛም ሕዋሳቱን በየዕለቱ እንዲቆርጡ አዘዘ የእጆቹንና የእግሮቹን ጣቶች ሃያውን ቆረጡ ክንዶቹንና እግሮቹን እስከ ጭኖቹ ድረስ ወደ አርባ ሁለት ቁራጭ በየጥቂቱ ቆረጡት ። በሚቆርጡትም ጊዜ ሁሉ ጌታዬና ንጉሤ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ዕንጨት ቅርንጫፍ ሰውነቴን በይቅርታህ ገናናነት ተቀበል የወይን አታክልት ያለው በየሦስት ዓጽቅ ሲቆርጡለት ዓጽቆቹ በዝተው ይበቅላሉ ይሰፋሉ በሚያዝያ ወር አብቦ ያፈራልና እያለ የሚዘምርና የሚያመሰግን ሆነ ።

ደረቱና አካሉ እንደ ግንድ ድብልብል ሆኖ በቀረ ጊዜ ነፍሱን ለመስጠት እንደ ደረሰ አውቆ በዚያን ጊዜ በዓለም ውስጥ ያሉትን ሰዎች ሁሉንም ይምራቸው ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነው እንዲህም አለ ለእኔ ግን ወደ አንተ የማነሣው አካል አልቀረልኝም ሕዋሳቶቼ ተቆርጠው በፊቴ የወደቁ ስለሆነ አሁንም ነፍሴን ተቀበላት አለ ።

በዚያንም ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ አረጋጋው አጸናውም ያን ጊዜ ነፍሱ ደስ አላት ነፍሱንም ከመስጠቱ በፊት ወታደሩ በፍጥነት መጥቶ የከበረች ራሱን በሰይፍ ቆረጠ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ ሥጋውንም ምእመናን ሰዎች ወስደው በመልካም አገናነዝ ገነዙትና በንጹሕ ቦታ አኖሩት ። እናቱ ሚስቱና እኅቱ በሰማዕትነት እንደሞተ በሰሙ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ወደ ቅዱስ ያዕቆብም ሥጋ መጥተው ተሳለሙት አለቀሱለትም የከበሩ ልብሶችንም በላዩ አኖሩ ጣፋጮች የሆኑ ሽቱዎችንም ረጩበት ።

በደጋጎች ነገሥታት በአኖሬዎስና በአርቃዴዎስ በሌሎችም ዘመን አብያተ ክርስቲያን ታነፁ ገዳማትና አድባራትም ተሠሩ የሰማዕታትንም ሥጋ በውስጣቸው አኖሩ ታላላቆች ድንቆች ተአምራትም ከእሳቸው የሚታዩ ሆኑ ። የፋርስ ንጉሥም ሰምቶ በቦታው ሁሉ የሰማዕታትን ሥጋ ያቃጥሉ ዘንድ አዘዘ በሚገዛውም አገር ውስጥ ምንም ምን እንዳይተው አማንያን ሰዎችም መጥተው የቅዱስ ያዕቆብን ሥጋ ወደ ኢየሩሳሌም ወሰዱት ከዚያም ወደ ሀገረ ሮሀ ከሀገረ ሮሀም የከበረ ኤጲስቆጶስ ጴጥሮስ ወደ ግብጽ አገር ወደ ብሕንሳ ከተማ ወሰደው ። በዚያም ጥቂት ጊዜ ኖረ ከርሱ ጋርም መነኰሳት ነበሩ ከቀኑ እኩሌታም ሲጸልዩ የቅዱስ ያዕቆብ ሥጋ ከብዙ የፋርስ ሰማዕታት ሥጋ ጋር በአለበት ሰማዕታት አብረዋቸው ዘመሩ ባረኳቸውም ቅዱስ ያዕቆብም እግዚአብሔር እንዳዘዘ ሥጋዬ በዚህ ይኑር አለ ከዚህም በኋላ ተሠወሩ ።

ከዚህም በኋላ የከበረ ኤጲስቆጶስ ጴጥሮስ ወደ አገሩ ሊመለስ በወደደ ጊዜ ሥጋዬ በዚህ ቦታ ይኑር ያለውን የቅዱስ ያዕቆብን ቃል ተላልፎ የቅዱስ ያዕቆብን ሥጋ ወሰደ በዚያንም ጊዜ አስቀድሞ ወደ አመለከተው ቦታ ከእጆቻቸው መካከል ተመለሰ ከሥጋውም ታላላቅ የሆኑ ተአምራት ተገለጡ ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ፊልሞና_ሐዋርያ

በዚህችም ዕለት ከሰባ ሁለቱ አርድእት የአንዱ የፊልሞና የዕረፍቱ መታሰቢያው ነው።

ቅዱስ ፊልሞና ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ ሲሆን ብዙ ጊዜ "ጥዑመ - ቃል (አንደበቱ የሚጣፍጥ)" ተብሎ ይጠራል። በዘመነ ሐዋርያት በጣም ልጅ በመሆኑ እየተሯሯጠ ለአበው ይታዘዝ ነበር።

ጌታን አምኖ ተከትሎ ለሦስት ዓመት ከሦስት ወር ተምሮ፣ ከቅዱስ መንፈሱ ነስቶ፣ ከቅዱስ እንድርያስ ጋር ለስብከት ወጥቷል። ሃገረ ስብከቱም ልዳ ነበረች። እርሱ ሲያነብ (ሲያስተምር) ሰው ሁሉ በተመስጦ ይሰማው ነበር። ሊገድሉት የመጡ ወታደሮች እንኳ በተደሞ መግደላቸውን ይረሱት ነበር።

አንዳንድ ቀን ደግሞ ወፎችና ርግቦች ያደምጡት፣ ያወሩትም ነበር። ይህቺ ቀን ለቅዱስ ፊልሞና ዕለተ ዕረፍቱ ናት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ጢሞቴዎስ_ሰማዕት

በዚህችም ቀን በንሑር ከሚባል አገር ቅዱስ ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሁልጊዜ በጾም በጸሎት ተጠምዶ የሚኖር ነው ስሟ ሞራ የሚባል ሚስት አለችው እርሷም የአጎቱ ልጅ ናት በሥራዋ ሁሉ ደስ የምታሰኘው መልካም ሴት ናት።

እንደዚህም በፍቅርና በስምምነት ሲኖር ከከሀዲ ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ዘንድ የጣዖታት ቤቶች ይከፈቱ ዘንድ አብያተ ክርስቲያናት እንዲዘጉ ትእዛዝ ወጣ። ቅዱስ ጢሞቴዎስም ይህን ሰምቶ እጅግ ደስ አለው። እርሱ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ደሙን ያፈስ ዘንድ ይህን ዘመን ይጠብቀው ነበርና ለሚስቱም ሊሠራው ያሰበውን ነገራት እርሷም የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን አለች።

ከዚህም በኋላ መንገዱን ያቀናለት ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ ጌታችንም በዚያች ሌሊት በሕልሙ ተገልጾለት ወዳጄ ጢሞቴዎስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን እነሆ ከጻድቃኖቼ ቁጥር ውስጥ ቆጥሬሃለሁ አሁንም ተነሣ ሚስትህንም ይዘህ ወደ ብህንሳ ከተማ ሒዳችሁ ጣዖታትን በሚያመልኩ ሁሉ ሕዝብ ፊት በስሜ ታመኑ አለው። በነቃ ጊዜም ለሚስቱ ነገራት እርሷም ይህንኑ የሚመስል ሕልሟን ነገረችው።

ከዚህም በኋላ ተነሥተው በአንድነት ሔዱ ወደ መኰንኑ ወደ ቊልቊልያኖስም ደረሱ መሰንቆና እንዚራ እያስመታ ለጣዖታቱ በዓልን ሲያከብር አገኙት ያንጊዜ ወታደሮቹ ይዘው በመኰንኑ ፊት አቆሙት ሚስቱም ተከተለችው መኰንኑም ለጣዖት መስገድን እያግባባ በርኅራኄ ቃል ተናገረው ቅዱሱ ግን እርሱንና የረከሰች ሃይማኖቱን ሰደበ ስለዚህም መኰንኑ ተቆጥቶ ከሚስቱ ጋር ወደ ወህኒ ቤት እንዲአስገቡት አዘዘ።

ከጥቂት ቀኖች በኋላም ከሚስቱ ጋር አውጥተው ደማቸው እንደ ውኃ እስቲፈስ በአለንጋዎች እንዲገረፉአቸው አዘዘ ያለ ርኅራኄም ገረፏቸው ሚስቱም በዚህ ሥቃይ ምስክርነቷን ፈጸመች።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Dec, 20:23


ሲጸልዩ ቅዱሳን መላእክት መጥተው በክንፋቸው ይጋርዷቸው ነበር፡፡ የአቡቀለምሲስን ራእይ በጸለዩ ጊዜ ራሱ ዮሐንስ ወንጌላዊው መጥቶ በአጠገባቸው ይቆም ነበር፡፡

አባታችን የዕረፍታቸው ጊዜ በደረሰ ሰዓት የብርሃን እናቱ እመቤታችን ሚካኤልንና ገብርኤልን ሰማዕቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን አስከትላ መጥታ "የጳውሎስ አበባ የጴጥሮስ ፍሬ የልጄ ተክል ወዳጄ ተክለ ሐዋርያት ሆይ ሰላምታ ይገባሃል" አለቻቸው፡፡ ዳግመኛም "እነሆ የተመኘኸውን ታገኘዋለህና፣ ጊዜው ቀርቧልና ጽና በርታ እኔንና ልጄን የለመንከንን ነገር አስብ" ብላቸው ተሰወረች፡፡ አባታችን በተደጋጋሚ እመቤታችንንና ጌታችንን ስለ ስሙ ብለው ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ ይለምኑ ስለነበረ ነው እመቤታችን ይህንን የነገረቻው፡፡

ከዚህም በኋላ የንጉሡ የዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ባለቤት አባታችንን "ስለ ክርስቶስ ብለሁ መጥተው አስትምሩን ምከሩን" ብላ ለመነቻቸውና አባታችን ሄደው መከሯት፡፡ ልጃቸውን ገላውዴዎስን አስተምረው ባረኩት፡፡ ለንጉሡ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብም ብዙ ምሥጢርን ነገሩት፡፡ ንጉሡም በአቅራቢያው የእመቤታችን ታቦት ካለችበት ቦታ ሦስት ወር ከእርሱ እንዲቀመጡ ለመናቸው፡፡ እሳቸውም በዚያ ሲቆዩ የንጉሡ ወታደሮች በፈረስ ግልቢያና በድብደባ እየተገዳደሉ አይተው አዘኑ፡፡ "ይህ የአረመኔዎች ሥራ ነው" ብለው ሕግንና ሥርዓትን ሊያስተማሯቸው አስበው ወደ ንጉሡ ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ እንዲያናግራቸው መልእክተኛ ላኩበት፡፡ ንጉሡም "ዛሬ አይመቸኝም" አላቸው፡፡ አባታችንም መልአክተኛውን ስለ ሰዎቹ በከንቱ መሞትና ሌላንም መልእክቶችን ላኩለት፡፡ መልእክተኛውም የመዘምራን አለቃ ደብተራ ስለነበር አባታችንን "እኔ እያለሁ ለአንተ ነቢይነትን ማን ሰጠህ?" ብሎ በክፉ ቃል ተናገራቸውና ሄዶ ከንጉሡ ጋር በክፉ ወሬ አጣላቸው፡፡ ወደ ንጉሡ ገብቶ "ንጉሥ ሆይ ይህ መነኩሴ ጻድቅ ነኝ ይላል፣ አንተን ግን ይሰድብሃል ባንተ ላይም ብዙ ዘለፋ ይናገራል…" አለው፡፡ ንጉሡም በጣም ተቆጥቶ አባተችን አስመጥቶ "ለምን ይዘልፉኛል?" አላቸው፡፡ አባታችንም ዘለፋ ሳይሆን ሊሆን የማይገባውን ነገር ሁሉ ነገሩት፡፡ ይልቁንም ስለሴቶቸና ስለፍርድና መሥራት ስለማይገባው ነገር ሁሉ ሲናገሩት ንጉሡም ደፍረው ስለተናገሩት በኃይል ይደበድቧቸው ዘንድ አዘዘ፡፡ ከአፍና አፍንጫቸውም ደም እንደውኃ እስኪርድ ድረስ ደበደቧቸውና አሠሯቸው፡፡

ዳግመኛም ንጉሡ ቢያስመጣቸው ደግመው ስለጥፋቱ ገሠጹት፡፡ አሁንም ጽኑ ድብደባን አደረሱባቸውና አሠሯቸው፡፡ በዚያም ብዙ አሠቃዩአቸው፡፡ በዚህም ጊዜ እመቤታችን ለአባታችን ለተልጣላቸው "እነሆ የልጄን ትእዛዝ ፈጸምህ የተመኘኸውን አገኘህ፣ ነገር ግን ሁለት የትዕግስት በር ይቀርሃል እርሱን ከፈጸምክ ልጄ ከዚህ ከኃላፊው ዓለም ያሳርፍሃል" አለቻቸው፡፡ አባታችንም እመቤታችንን "ሰማዕትነት ስጪኝ ያልኩሽ በክርስቲያናዊ እጅ ነውን? ነገር ግን አማላጅነትሽ ሰማዕትነትን ለመፈጸም ያጽናኝ" አሏት፡፡

ከዚህም በኋላ የንጉሡ ጭፍሮች አባታችንን በጠጠር ጎዳና ላይ እየጎተቷቸው ብዙ አሠቃዩአቸው፡፡ የንጉሡ ስምንት ጭፍሮች በመቀጣጠብ "ንጉሡ መቼ እሞታለሁ" ብሎሃል እያሉ በመሾፍ አባታችንን ወደ ዱር ወስደው በአቅማቸውን ያህል በኃይል ደበደቧቸው፡፡ የመንፈስ ቅዱስ ኃይል ባያጸናቸው ኖሮ በአንደኛው ሰው ዱላ ብቻ ነፍሳቸው በወጣች ነበር፡፡ በእሥርም 8 ወር ከተቀመጡ በኋላ ከዚህ ዓለም በሞት የሚያርፉበት ጊዜ ስለደረሰ ቅዱሳን መላእክት ከእሥር ቤት ነጥቀው ወስደው ወደ ሰማይ አሰረጓቸውና በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቆሟቸው፡፡ በዚያም ለሦስት ሳምንት ቆዩ፡፡ ጌታችንም ለአባታችን ብዙ የሕይወትን ምሥጢር ነገራቸው፡፡ እንደጸሐይ የምታበራዋን የምድርን ማዕዘነ ዓለም የምታክል ሰማያዊት ሀገር ርስት አድርጎ ሰጣቸው፡፡ "ስምህን ከሚጠሩ ልጆችህ፣ የገድልህን መጽሐፍ ከጻፉ ካጻፉ ከሰሙ፣ ዝክርን ካዘከሩ በጸሎትህ ከተማኑ ልጆችህ ጋር የምትኖርባት ዕድል ፈንታህ ናት" አላቸው፡፡

አባታችንም ጌታችንን "አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ ይህን ቃልኪዳን የሰጠኸኝ አንተን የሚያስደስት ምን ነገር አደረኩልህ በቸርነትህ ነው እንጂ" አሉት፡፡ ጌታችንም "ዕድል ፈንታህ ጽዋ ተርታህ እውነተኛ የእኔ ምስክር ከሚሆን ጊዮርጊስና ወዳጄ ከሚሆን ከዮሐንስ ጋራ ይሁን" አላቸው፡፡ ዳግመኛም ጌታችን ሰባት አክሊትን አቀዳጃቸውና "አንዱ ስለ ድንግልናህ ነው፣ አንዱ ሃይማኖትህን ለማስተማር ከአንዱ ሀገር ወደ አንዱ አገር ስለሄድክ ነው፣ አንዱ ቅዱሳንን ለመጎብኘት እየተዘዋወርክ ከቅዱሳን ጋራ ስለተነጋገርክበት ነው፣ አንዱ ስለየዋህነትህ ኃላፊ ዓለምን ስለመናቅህ ነው፣ አንዱ ስለተወደደ ክህነትህ ነው፣ አንዱ ታግሰህ ስለመጋደልህ ነው፣ አንዱም ደምህን ስለማፍሰስህ ነው" አላቸው፡፡ ጌታችን ይህን ቃልኪዳንና ክብር ከሰጣቸው በኋለ "ከዚህ ከሚጠፋው ዓለም አሳርፍሃለሁ" አላቸው፡፡ ከዚህም በኋላ ከተነጠቁበት ከሦስት ሳምንት በኋላ ተመልሰው ከእሥር ቤቱ ሆነው ያዩትን ሁሉ ለአንድ ወዳጃቸው ለሆነ ቄስ ተክለ ኢየሱስ ነገሩት፡፡

ዳግመኛም አባታችን በእሥር ቤት ሳሉ በመላአክት እጅ ተነጥቀው ወደ ሰማይ ከተወሰዱና ከጌታችን ቃልኪዳን ከተቀበሉ በኋላ የብርሃን እናቱ ክብርት እመቤታችን እንዳነጋገረቻቸው ተናገሩ፡፡ "እመቤታችን ማርያም 'ዘርዐ ያዕቆብን ይቅር በልልኝ፣ ኃጢአቱንም ተውለት፣ በልጄ ፊት ቀርበህ 'ግፌን ተመልከትልኝ' አትበል እርሱ ዘወትር ስሜን ይጠራልና፣ ስለ ድንግልናዬም የሚያስተምር ነውና' አለኝ፡፡ እኔም የእመ ብርሃንን ርኅራኄ አደነቅሁና 'እመቤቴ ሆይ! አንቺ እያዘዝሽኝ ወድጄ ነውን የምመረው! እኔ ኃጢአተኛ ለምን ይቅር አልልም ይቅር እላለሁ እንጂ ነገር ግን የአንቺ ጸሎት ሁላችንንም ይማረን' አልኋት፡፡"

አቡነ ተክለ ሐዋርያት በመጨረሻ ዘመናቸው በንጉሡ አደባባይ ኅዳር 27 ቀን ሲያርፉ ቅዱሳን መላእክት መጥተው ገንዘው ቀብረዋቸዋል፡፡ በመካነ መቃብራቸውም ላይ ብርሃን ተተክሎ ታይቷል፡፡ ንጉሡ ዘርዐ ያዕቆብም በመካነ መቃብራቸው ላይ ብርሃን መውረዱንና ብዙ ተአምራት ማድረጉን በሰማ ጊዜ እጅግ አደነቀ፡፡ ብዙ ምልክትም አገኘ፡፡ አባታችን ሰማዕትነትን ይቀበሉ ዘንድ ተመኝተው ራሳቸው ለምነዋልና መደብደብ መሠቃየታቸው በእግዚአብሔር ፈቃድ ነው፡፡ ንጉሡም መነኮሳት ልጆቻቸውንም ጠርቶ የአባታችንን ሥጋ በክብር እንዲያፈልሱ ነገራቸው፡፡ ርስት ጉልት የሚሆን መሬት ሰጣቸው፡፡ ነገር ግን ዐፅማቸው ከመፍለሱ በፊት ንጉሡ በሞት ስላረፈ ልጁ በእደ ማርያም በአባቱ ትእዛዝ መሠረት የአባታችንን ዐፅም ከ13 ዓመት በኋላ ወደ ደብረ ጽሞና በክብር አፍልሶታል፡፡ ታቦታቸው ደብረ ሊባኖስ አውራጃ አጋት መድኃኔዓለም ይገኛል፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘግሙድ

ዳግመኛም በዚህች ቀን ለፋርስ ንጉሥ ለሳፎር ልጅ ለንጉሥ ሰክራድ ከጭፍሮቹ ውስጥ የሆነ ሕዋሳቱን የተቆራረጠ ቅዱስ ያዕቆብ በሰማዕትነት አረፈ።

ይህም ንጉሥ ሰክራድ እጅግ ይወደው ነበር ስለ መንግሥቱ ሥራ ሁሉ ከእርሱ ጋር ይማከር ነበርና ስለዚህም የቅዱስ ያዕቆብን ልቡና አዘንብሎ ፀሐይንና እሳትን እንዲአመልክ አደረገው ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Dec, 20:23


#ኅዳር_27

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ኅዳር ሃያ ሰባት በዚህች ቀን አባታችን #አቡነ_ተክለ_ሐዋርያት ዕረፍታቸው ነው፣ ሕዋሳቱ የተቆራረጠ #ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘግሙድ በሰማዕትነት አረፈ፣ ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ #ቅዱስ_ፊልሞና_ሐዋርያ ዕረፍቱ ነው፣ በንሑር ከሚባል አገር #ቅዱስ_ጢሞቴዎስ በሰማዕትነት አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ተክለ_ሐዋርያት

ኅዳር ሃያ ሰባት በዚህች ቀን አባታችን አቡነ ተክለ ሐዋርያት በክብር አርፈዋል።

አባታቸው የእናርዕት አገረ ገዥ የነበሩት እንድርያስ ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ እሌኒ ይባላሉ፡፡ የትውልድ ሀገራቸው ሸዋ ሲሆን በዚሁ የምትገኘውን ታላቋን የደብረ ጽሙናን ገዳም የመሠረቱ ሲሆን በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ዘመን የነበሩ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ ገና በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ አጋንንትን እያቃጠሉ ያጠፏቸው ነበር፡፡ የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ተምረው ከጨረሱ በኋላ ገና በድቁና እያገለገሉ ሳለ 40 ቀን በማክፈል ይጾሙና ይጸልዩ ነበር፡፡

አባታችን የመነኮሱትና ብዙ ተጋድሎአቸን ፈጽመው ወደ ሰማይ ተነጥቀው ሥላሴን እስከማየት የደረሱት በደብረ ሊባኖስ ነው፡፡ ያመነኮሷቸውም ሁሉን በስውር ያለውን የሚውቁት አቡነ ዮሐንስ ከማ ናቸው፡፡ አባታችን ማታ ማታ ከባሕር ውስጥ ገብተው ሲጸልዩ እያደሩ በቀን 30 ፍሬ አተር ብቻ እየተመገቡ ይጾሙ ነበር፡፡ ስውራን የሆኑ ቅዱሳን አባታችም እየተገለጡላቸው ምሥጢራትን ይነግሯቸዋል፡፡ ከስግደታቸውም ብዛት የተነሣ የአባታችን ሁለት የእጆቻቸው አጥንቶች ተሰበሩ፡፡ ከቁመታቸውም ብዛት የተነሣ እግሮቻቸው አበጡ፡፡ ስምንት ስለታም ጦሮችን ያሉበትን የብረት ሰንሰለት በወገባቸው ታጥቀው ሁለት ሁለቱን በፊት በኋላ በቀኝ በግራ አድርገው ታጠቁ፡፡ እነዚህም ጦሮች ከልደት፣ ከጥምቀትና ከትነሣኤ በዓል በቀር ከወገባቸው ላይ አያወጧቸውም ነበር፡፡

በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ሲቀመጡ፣ ሲነሡና ሲሰግዱ ጦሮቹ ሰውነታቸውን ሲወጓቸው በዚያን ጊዜ የጌታችንን በጦር መወጋቱንና መከራውን ያስባሉ፡፡ በታመሙም ጊዜ "ኃጢአተኛ ሰውነቴ ሆይ ስለአንቺ የተቀበለውን የክርስቶስን መከራ አስቢ" እያሉ ሰውነታቸውን ይጎስማሉ፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነጥቆ ወስዶ ከገነት ዕፅ አምጥቶ አባታችንን ካሸታቸው በኋላ ግን ርሃብና ጥም የሚባል ነገር ጠፍቶላቸዋልና ምድራዊውን ነገር ለመቅመስ የሚጸየፉ ሆኑ፡፡ ጻድቁ ቅስና እንዲሾሙ የገዳሙ አበምኔት ግድ ቢሏቸውም አባታችን ግን እምቢ ስላሉ "ለጳጳሱ መልእክት አድርስልኝ" ብለው በዘዴ ልከዋቸው ጳጳሱም በመንፈስ ተረድተው ቅስና ሾመዋቸዋል፡፡

ጻድቁ በአቡነ አትናቴዎስ መቃብር ላይ ሄደው አጥብቀው ይጸልዩ በነበረበት ወቅት ብርሃን ይወርድላቸው እንደነበር እግዚእ ክብራ የተባለች አንዲት ትልቅ ጻድቅ እናት ትመለከት ነበር፡፡ አባታችን ሁልጊዜ "ሦስት ነገሮችን እፈልጋለሁ እነርሱም ከሐሜት ስለመራቅ፣ ክፉ ነገርን ከማየት ስለመራቅና ከንቱ ነገርን ከመስማት ስለመራቅ ናቸው" እያሉ ይናገሩ ነበር፡፡ አቡነ ተክለ ሐዋርያት የታላቁን አባት የአቡነ አትናቴዎስን መቃብር ለማየት በሄዱ ጊዜ ቆመው ሲጸልዩ ከእግራቸው በታች ጸበል ፈልቆ በጽዋ ውኃ ሲፈስ አገኙት፡፡ ውኃውንም ወስደው ቦታውን ላሳየቻቸው ለእግዚእ ክብራ ሰጧት፡፡ እርሷም መካን ለነበረችው ገረዷ ሰጠቻትና ገረዷም በጻድቁ ጸሎት የፈለቀውን ውኃ ጠጥታ ልጅ ወለደች፡፡ ይህ አባታችን ያፈለቁት ጸበል ዛሬም ድረስ ሲፈስና ሕሙማንን ሲፈውስ ይገኛል፡፡

ጸድቁን የታዘዘ መልአክ መጥቶ ወደ በረሃ እንዲገቡ ስለነገራቸው ወደ ምድረ ሐጋይ ሄደው በዚያ ታላቅ በረሃ ውስጥ ለ41 ዓመታት ጽኑ ተጋድሎን ተጋድለዋል፡፡ ባሕር ውስጥ በሚገኝ ዋሻ ውስጥም ገብተው ብዙ ዘመን በጸሎት ኖረዋል፡፡ ሰዎች የአባታችንን የእግራቸውን እጣቢ ሕመምተኞች ላይ በረጩት ጊዜ በላያቸው ላይ ያደረባቸው ርኩስ መንፈስ እየጮኸ ይወጣል፡፡ ቅዱሳን መላእክት ዘወትር እየመጡ አባታችንን ይጎበነኟቸዋል፡፡ እመቤታችን ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስን አስከትላ እየመጣች ትጎበኛቸዋለች፡፡ ብዙ ተጋድሎ ባደረጉበት ዋሻ ውስጥም ሳሉ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ተገልጦላቸው በቦታው ላይ ታላቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸዋል፡፡ መላእክትም ወደ ሰማይ አሳርገዋቸው በሥሉስ ቅዱስ መንበር ፊት አቁመዋቸው ታላቅ ምሥጢርን አይተዋል፡፡

አቡነ ተክለ ሐዋርያት ለመድኃኔዓለም ሥጋና ደም ትልቅ ክብር ያላቸው አባት ናቸው፡፡ አንድ በከባድ በሽታ ይሠቃይ የነበረ ሰው "ነፍሴ ከሥጋዬ ሳትለይ ፈጥናችሁ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውሰዱኝና የጌታችንን ሥጋና ደም ልቀበል" ብሎ ቤተሰቦቹን ለመነ፡፡ ቤተሰቦቹም ወደ ቤተ ክርስቲያን ወስደውት ሥጋ ወደሙን ከተቀበለ በኋላ ከሆዱ ውስጥ ዥንጉርጉር ደምና ሐሞት ከመግል ጋር ወጣ፡፡ በዚህም ጊዜ ካህናቱ ስለ ሥጋ ወደሙ ክብር ብለው በዕቃ ተቀበሉት፡፡ ሽታው ግን ቤተ ክርስቲያኑን አናወጸው፡፡ በዚህም ጊዜ አባታችን ተክለ ሐዋርያት መድኃኔዓለም ክርስቶስ ስለእኛ ብሎ በዕለተ ዐርብ መራራ ሐሞትና ከርቤ መጠጣቱን አስበው ከሰውየው ሆድ ውስጥ የወጣውን ደም የተቀላቀለበትን መግልና ሐሞት ስለ ሥጋ ወደሙ ክብር ብለው በቤተ ክርስቲያኑ በተሰበሰቡት ሰዎች ፊት አንሥተው ጠጡት፡፡ ይህም የሆነበት ዕለት እሁድ ነበርና አባታችን እዚያው ቤተ ክርስቲያኑ ዋሉ፡፡ መድኃኔዓለም ክርስቶስም አባታችን ወዳሉበት መጥቶ "ወዳጄ ተክለ ሐዋርያት ሆይ ሰላምታ ይገባሃል፡፡ በሰው ሁሉ ፊት እንዳከበርከኝ እኔም በምድራውያንና በሰማያውያን መላእክት ሁሉ ፊት አከብርሃለሁ" ካላቸው በኋላ ሌላም ብዙ ቃልኪዳን ገባላቸው፡፡ ሰባት አክሊላትንም ካቀዳጃቸው በኋላ ዕጣ ክፍላቸው ከመጥምቁ ዮሐንስና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር መሆኑን ነግሯቸዋል፡፡

ከዚህም በኋላ አባታችን ወደተለያዩ የሀገራችን ገዳማት በመሄድ ከቅዱሳን በረከትን ከተቀበሉ በኋላ በየሄዱባቸው ገዳማት 40 ቀንና 40 ሌሊት ይጾማሉ፡፡ ከሰንበት በቀርም ምንም ምንመ አይቀምሱም፡፡ ሰንበትም በሆነ ጊዜ የዕንጨቶችን ፍሬ ብቻ ይመገባሉ፡፡ አባታችን ከዋልድባ ገዳም ወጥተው ወደ ደባብ ገዳም በመሄድ በዚያ አርባዋን ቀን ከጾሙ በኋላ ጌታችን ተገለጠላቸውና "ተነሥተህ ወደ አልተጠመቁ አሕዛብ አገር ሂድ በዚያ በአንተ እጅ የሚጠመቁና የሚድኑ ብዙ አሕዛብ አሉና በስሜ አስተምር" አላቸው፡፡ አባታችንም ተነሥተው "ሀገረ ጽልመት" ወደሚባል ወዳልተጠመቁ አሕዛብ አገር ሄደው የአገሪቱን ንጉሥና ሕዝቡንም በጠቅላላ አስተምረው በተአምራቶቻቸው አሳምነው አጥምቀዋቸዋል፡፡ በዚያም ሀገር ለአሕዛብ እየጠነቆለ የሚኖር አንድ መሠርይ ነበርና አባታችንን አግኝተውት አስተምረው በላዩ ያለበትን ርኩስ መንፈስ አውጥተውለት አጥምቀውታል፡፡

አባታችን የእግዚአብሔርን ወዳጅ የሊቀ ነቢያትን መቃብር ያሳቸው ዘንድ ጌታችንን በለመኑት ጊዜ ጌታችን በሌሊት ተገልጦላቸው ወስዶ የሙሴን መቃብር አሳይቷቸዋል፡፡ የአባታችን በትራቸው እንደሙሴ በትር ተአምር ትሠራ ነበር፡፡ ሕመምተኞች በትሯን አጥበው የእጣቢውን ውኃ ሲጠጡት ፈጥነው ከሕመማቸው ይፈወሱ ነበር፡፡ በጌታችን የጥምቀት በዓል ቀን አባታችን ተክለ ሐዋርያት ጸሎት በማድረግ ሰዎችን ሲያጠምቁ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሳቸው ላይ ይታይ ነበር፡፡ በቆሙበትም ቦታ የብርሃን ምሰሶም እስከ ሰማይ ድረስ ደርሶ ተተክሎ ታይቷል፡፡ አባታችን ቅዱሳት ገዳማትን ለመሳለም ከአንዱ ቦታ ወደ አንዱ ቦታ የሚዘዋወሩት በብርሃን ሰረገላ ነበር፡፡ በደመናም ተጭነው ሲሄዱ ያዩአቸው ቅዱሳን አሉ፡፡ የመኮትን ቃል ወንጌልን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Dec, 13:29


https://t.me/onewin_pay_bot?start=_tgr_t5EQk7E0YWE0

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Dec, 09:36


✝️እባካችሁ ልታይ ልታይ አትበሉ!!



[መ/ር ኢዮብ ይመኑ]



ሠናይ ቀን ቤተሰብ🙏

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Dec, 03:31


"ልማት ማለት መሬትን መቆፈር ብቻ አይደለም፣የሰውን ልቦና በትምህርተ ወንጌል ቆፍሮ ማለምለም፣ በሰው አእምሮ ፍቅርና ስምምነትን መዝራትና መትከል፣ሰውን ከስህተት መመለስና ማስተማር ከልማቶች ሁሉ የበለጠ ነው

{ ብጹዕ አቡነ ጳውሎስ }



እንደምን አደራችሁ አረፈዳችሁ ቤተሰብ🌹

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Nov, 19:33


#ኅዳር_16

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ኅዳር ዐሥራ ስድስት በዚህች ቀን #የቅዱስ_አቡናፍር ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ነው፣ የእስክንድርያ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ዮሐንስ ያረፈበት ነው፣ #ቅዱስ_ኪስጦስ በሰማዕትነት ያረፈበት ነው፣ #ቅድስት_ጣጡስ በሰማዕትነት ያረፈችበት ነው፣ የመነኰስ #አባ_ዳንኤልና_የንጉሥ_አኖሬዎስ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አቡናፍር

ይኸውም ቅዱስ አቡናፍር ጥቂት የሰሌን ፍሬዎችን ብቻ እየተመገበ በበረሃ ውስጥ 60 ዓመት የኖረ ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡ በእነዚህ ድፍን 60 ዓመታት ውስጥ ከቶ የሰውን ፊት አላየም፡፡ ዛሬ ከምስር ከተማ ውጪ የተሠራች ቤተ ክርስቲያኑ የከበረችበት ዕለት ነው፡፡

አቡነ አቡናፍር መልካም ሽምግልና ያለው ስም አጠራሩ የከበረ በገዳም የሚኖርና በገድል የተጠመደ አባት ነው፡፡ ከላይኛው ግብፅ የተገኘ ሲሆን ታሪኩን የተናገረለት ጻዲቁ አባ በፍኑትዮስ ነው፡፡ ይኸውም አባ በፍኑትዮስ ወደ በረሃ ውስጥ በገባ ጊዜ አንዲት የውኃ ምንጭና አንዲት የሰሌን ምንጣፍ አግኝቶ በዚያ እየተጋደለ ብዙ ዘመን የኖረ ነው፡፡

በአንዲት ዕለት አባ በፍኑትዮስ ወደ እርሱ ሲመጣ አባ አቡናፍር አየው፡፡ አባ በፍኑትዮስም የሰይጣንን ምትሐት የሚያይ መስሎት ደነገጠ፡፡ አባ አቡናፍር ፀጉሩና ጽሕሙ ሰውነቱን ሁሉ ሸፍኖታል እንጂ በላዩ ላይ ልብስ አልነበረውም፡፡ አባ በፍኑትዮስንም በመስቀል ምልክት ባርኮ አጽናናው፡፡ አቡነ ዘበሰማያትንም ከጸለየ በኋላ ‹‹አባ በፍኑትዮስ ሆይ ወደዚህ መምጣትህ መልካም ነው›› ብሎ በስሙ ከጠራው በኋላ ፍርሃቱን አራቀለት፡፡

ከዚህም በኋላ ሁለቱም በጋራ ጸልየው የእግዚአብሔርን ገናናነት እየተነጋገሩ ተቀመጡ፡፡ አባ በፍኑትዮስም አኗኗሩንና እንዴት ወደዚህ በረሃ እንደመጣ ታሪኩን ይነግረው ዘንድ አባ አቡናፍርን ለመነው፡፡ አባ አቡናፍርም ታሪኩን እንዲህ ብሎ ነገረው፡- "እኔ ደጋጎች እውነተኞች መነኮሳት በሚኖሩበት ገዳም ውስጥ እኖር ነበር፡፡ የገዳማውያንን ልዕልናቸውን ሲናገሩ ሲያመሰግኗቸውም ሰማሁ፡፡ እኔም ‹ከእናንተ የሚሻሉ አሉን?› ብዬ ጠየኳቸው፡፡ እነርሱም ‹አዎን እነርሱ በበረሃ የሚኖሩ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበሩ ናቸው፤ እኛ ለዓለም የቀረብን ስለሆንን ብንተክዝና ብናዝን የሚያረጋጋን እናገኛለን ብንታመም የሚጠይቀንና የፈለግነውን ሁሉ እናገኛለን፣ በበረሃ የሚኖሩ ግን ከዚህ ሁሉ የራቁ ናቸው› አሉኝ፡፡ ይህንንም ስሰማ ልቤ እንደ እሳት ነደደና ወደ ፈቀደው መንገድ ይመራኝ ዘንድ በእኩለ ሌሊት ተነሥቼ ጸለይኩ፡፡ ከዚህም በኋላ ተነሥቼ ወጥቼ ስጓዝ አንድ አባት አገኘሁና የገዳማውያንን ገድላቸውን እያስተማረኝ ከእርሱ
ጋር ተቀመጥኩኝ፡፡ ከዚያም ወደዚህ ቦታ ደረስኩ፡፡ እግዚአብሔር ያዘጋጀልኝን ይህችን ሰሌን አገኘኋት፡፡ በየዓመቱ 12 ዘለላ ታፈራለች፤ ለየወሩም የምመገበው አንዱ ዘለላ ይበቃኛል ውኃም ከዚህች ምንጭ እጠጣለሁ፡፡ በዚህችም በረሃ እስከዛሬ 60 ዓመት ኖርኩ፡፡ ከአንተም በቀር የሰው ፊት ከቶ አይቼ አላውቅም" ብሎ አቡነ አቡናፍር ጣፋጭ ታሪኩን በዝርዝር ነገረው፡፡ ይህንንም ሲነጋገሩ የታዘዘ መልአክ መጥቶ የጌታችንን ሥጋና ደም አምጥቶ አቆረባቸው፡፡ ቀጥለውም ጥቂት የሰሌን ፍሬ ተመገቡ፡፡ ወዲያውም የአቡነ አቡናፍር መልኩ ተለወጠ፤ እንደ እሳትም ሆነ፡፡ ወደ እግዚአብሔርም በተመስጦ እየጸለየ ሳለ ቅድስት ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፡፡

አቡነ በፍኑትዮስም በፀጉር ልብሱ በክብር ገንዞ ቀበረው፡፡ ከዚህም በኋላ አባ በፍኑትዮስ በዚያች ቦታ ይኖር ዘንድ ወደደ ነገር ግን ያቺ የሰሌን ዛፍ ወደቀች፤ የውኃዋም ምንጭ ደረቀች፡፡ አባ በፍኑትዮስም ወደ ዓለም ተመልሶ የገዳማውያንን ዜና ይልቁንም የአባ አቡናፍርን ዜና ይሰብክ ዘንድ የእግዚአብሔር ፍቃድ ሆነ፡፡

የአቡነ አቡናፍር ዕረፍታቸው ሰኔ 16 ቀን ነው፡፡ ኅዳር 16 ደግሞ ከምስር ከተማ ውጪ የተሠራች ቤተ ክርስቲያናቸው የከበረችበት ዕለት ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባት_አባ_ዮሐንስ

በዚህችም ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ስምንተኛ የሆነ የእስክንድርያ ሀገር ሊቀ ጳጳሳት ቅዱስ አባት አባ ዮሐንስ አረፈ። ይህም ቅዱስ አባት የቆጵሮስ ሀገር ሰው ነው እጅግም ባለጸጋ ነው በእስክንድርያ አገርም የሚኖር ሆነ አባቱ አገረ ገዥ ነበርና ሚስትም አግብቶ ልጆችን ወለደ ከዚህም በኋላ ሚስቱም ልጆቹም ሞቱ።

በዚያንም ጊዜ ገንዘቡን ሁሉ ለድኆችና ለችግረኞች ሰጠ መጸወተ እርሱም መንኵሶ በታላቅ ገድል የተጠመደ ሁኖ በጎ ሥራዎችን ትሩፋትን ጨምሮ በመሥራት እግዚአብሔርን ደስ አሰኘው።

ከበጎ ሥራዎቹና ከትሩፋቱም ከቀናች ሃይማኖቱ ከአገልግሎቱና ከደግነቱ ከጽድቁ ማማር የተነሣ በግብጽ አገር የሚኖሩ ኤጲስቆጶሳት ሁሉም ተሰማምተው ይዘው ወሰዱት ያለ ፈቃዱም በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙትና በወንጌላዊ ማርቆስ ወንበር ላይ አስቀመጡት ። ያን ጊዜ የከበረ ወንጌልን አነበበ በሹመቱና በክህነቱም ብርሃን ተገለጸ ብዙዎች ድንቆች የሆኑ ተአምራትንም አደረገ።

ለድኆችና ለችግረኞች ሁልጊዜ ያለማቋረጥ የሚሹትን የሚሰጣቸው ሆነ ስለዚህም የሚራራ ዮሐንስ ተብሎ ተጠራ ። በአይሁድና በአረማውያን ዘንድ የሚአስፈራ ሆነ በመጸሐፈ ገድሉ እንደተጻፈ እጅግ ይፈሩትና ያከብሩት ነበርና መንጋዎቹንም በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ኪስጦስ

በዚችም ቀን ቅዱስ ኪስጦስ በመኰንኑ በመክሲሞስ እጅ በሰማዕትነት አረፈ ። ይህንንም ቅዱስ ኪስጦስን መኰንኑ በያዘው ጊዜ ጽኑዕ ሥቃይን አሠቃየው ከዚህም በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጠ የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅድስት_ጣጡስ

በዚችም ዕለት በሮሜ አገር በከሀዲ መኰንን በእስክንድሮስ እጅ ቅድስት ጣጡስ በሰማዕትነት አረፈች። ወደርሱም በአቀረቧት ጊዜ እስክንድሮስ ለአማልክት ሠዊ አላት እርሷም ከፈጠረኝ ከጌታዬ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር አልሠዋም ብላ መለሰች።

መኰንኑም የፊቷን መሸፈኛ እንዲገልጡ አዘዘ ውበቷንም አይቶ አደነቀ ዐይኖቿ እንደ አጥቢያ ኮከብ ናቸውና ቁመቷም እንደ ዘንባባ ደም ግባቷም እንደ ጽጌረዳ ነው በዚያንም ወራት የሚመሳሰላት የለም ነበር።

ንጉሡም በአያት ጊዜ እርሷን በመውደዱ ልቡ ተነጠቀ እንዲህም አላት እሺ በይኝና ለታላቅ አምላክ ለአጵሎን ሠዊ እኔም ለቤተ መንግሥቴ እመቤት አደርግሻለሁ አላት። ቅድስት ጣጡስም እኔ ክብር ይግባውና ከክርስቶስ ከመንጋዎቹ ውስጥ ነኝ ከእርሱ በቀር ለሌላ አልሠዋም ነገር ግን ወደ አማልክቶችህ መሠዊያ ቤት ገብቼ ኃይላቸውን እንዳይ ፍቀድልኝ አለችው።

በዚያንም ጊዜ ወሰዷት በገባችም ጊዜ ጣዖታቱ ይጠፉ ዘንድ ክብር ይግባውና የኃይል ባለቤት ወደ ሆነ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጸለየች ወዲያውኑ ንውጽውጽታ ሁኖ ጣዖታቱ ከመቀመጫቸው ወድቀው ተሰባበሩ ታላቁ አምላካቸው አጵሎንም ቊልቊል ወድቆ ተቀጠቀጠ ከጣዖቱ አገልጋዮችም ብዙዎች ሞቱ በአጵሎን ላይ አድሮ የሚኖር ርኩስ መንፈስ እንዲህ ብሎ ጮኸ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Nov, 09:13


አዲሱ ወጥመድ#ማህበራዊ ሚዲያ!!



#ሊቃዉንት ስምዖኮነ/ከመጋቤሐዲስ ነቅዓ ጥበብ



መልካም ዕለተ ሰንበት

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Nov, 06:59


# የማለዳ የሕይወት ቃል
✞ የሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ      
   
✍️:‹‹ስድስት ቀን ሥራ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ በሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ እግዚአብሔርም በሰባተኛው ቀን አርፏልና ስለዚህ እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን ባርኮታል ቀድሶታል››
❖ዘጸ 20፥10-11


ሠናይ ሰንበት
🥰

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Nov, 23:23


#ኅዳር_15

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ኅዳር ዐሥራ አምስት በዚህች ቀን #ቅዱስ_ሚናስ በሰማዕትነት አረፈ፣ የሕፃኑ ሰማዕት #ቅዱስ_ቂርቆስ ልደቱ ነው፣ ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_ሚናስ_ሁለተኛው ያረፈበትን ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ሚናስ_ሰማዕት

ኅዳር ዐሥራ አምስት በዚህች ቀን የስሙ ትርጓሜ ቡሩክና የታመነ የሆነ ቅዱስ ሚናስ በሰማዕትነት አረፈ። የዚህም ቅዱስ አባቱ አናቅዮስ ከሚባል አገር ነው ስሙም አውዶክስዮስ ነው እርሱም አገረ ገዥነት ተሹሞ ሳለ ወንድሙ ቀንቶበት በንጉሥ ዘንድ ነገር ሠራበት ንጉሡም ወደ አፍራቅያ አገር ሰደደውና በዚያም አገረ ገዢ አድርጎ ሾመው የአገር ሰዎችም ሁሉ ደስ አላቸው እርሱ ለሰው የሚራራ እግዚአብሔርንም የሚፈራ ደግ ሰው ነውና ።

እናቱም ልጅ አልነበራትም በአንዲት ዕለት ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በበዓልዋ ቀን ገብታ የክርስቲያንን ወገኖች ያማሩ ልብሶችን ለብሰው ከልጆቻቸው ጋር ደስ እያላቸው ሲገቡ አየቻቸው። በእመቤታችንም በቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ፊት አለቀሰች ልጅን ይሰጣት ዘንድ ወደ ልጅዋ ወደ እግዚአብሔር እንድትለምንላትም ለመነቻት በዚያንም ጊዜ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል አሜን የሚል ቃል ወጣ።

ከዚህም በኋላ ወደ ቤቷ ገብታ ይህን ቃል ለባሏ ነገረችው እርሱም የእግዚአብሔር ፈቃዱ ይሁን አለ። ከጥቂት ቀኖችም በኋላ እግዚአብሔር ይህን የተባረከና የከበረ ልጅን ሰጣት የእመቤታችንም ሥዕል ሚናስ ብላ እንደሰየመችው ስሙን ሚናስ ብለው ሰየሙት። ጥቂት በአደገ ጊዜም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩት። ዐሥራ ሁለት ዓመትም ሲሆነው በመልካም ሽምግልና አባቱ አረፈ ከእርሱም በኋላ በሦስተኛ ዓመት እናቱ አረፈች ቅዱስ ሚናስም ብቻውን ቀረ።

መኳንንቱም አባቱን አብዝተው ከመውደዳቸው የተነሣ ሚናስን በአባቱ ፈንታ ምስፍናን ሾሙት እርሱም የክርስቶስን አምልኮት አልተወም።

ዲዮቅልጥያኖስም በካደ ጊዜ ሁሉንም ሰዎች ጣዖታትን እንዲአመልኩ አዘዛቸው ብዙዎችም ክብር ይግባውና በክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ሞቱ ። በዚያንም ጊዜ ሚናስ ሹመቱን ትቶ ወደ ገዳም ገባ ታላቅ ተጋድሎን እየተጋደለ ብዙ ዘመናት ኖረ ። በአንዲትም ዕለት ሰማይ ተከፍቶ ሰማዕታትን የብርሃን አክሊሎችን ሲያቀዳጇቸው አየ። ስለ ክርስቶስ ስም በመከራ የደከመ ይህን አክሊል ይቀበላል የሚል ቃልን ሰማ። በዚያንም ጊዜ ወደ ከተማ ተመለሰና ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነ ሰዎችም አብዝተው አባበሉት በወገን የከበረ እንደሆነ እነርሱ ያውቁ ነበርና።

መኰንኑም ብዙ ቃል ኪዳን ገባለት ባልሰማውም ጊዜ ጽኑዕ በሆነ ሥቃይ እንዲአሠቃዩት አዘዘ። ማሠቃየቱንም በሰለቸ ጊዜ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ ። በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበለ ብዙዎችም በእርሱ ምክንያት ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በሰማዕትነት ሞቱ።

የቅዱስ ሚናስንም ሥጋ ወደ እሳት እንዲጥሉት መኰንኑ አዘዘ እሳትም አልነካውም ምእመናን ሰዎችም የቅዱስ ሚናስን ሥጋ ወስደው በአማሩ ልብሶች ገነዙት የስደቱ ወራትም እስከሚፈፀም በአማረ ቦታ ውስጥ አኖሩት።

በዚያንም ወራት የመርዩጥ አገር ሰዎች ከአምስቱ አገሮች ሠራዊትን ሊአከማቹ ወደዱ የቅዱስ ሚናስንም ሥጋ ረዳት ይሆናቸው ዘንድ በመንገድም እንዲጠብቃቸው ከእርሳቸው ጋር ወሰዱት።

እነርሱም በባሕር ላይ በመርከብ ውስጥ ሳሉ ፊታቸው እንደ ከይሲ አንገታቸው እንደ ግመል አንገት ያለ አውሬዎች ከባሕር ወጡ ይልሱትም ዘንድ ወደ ቅዱስ ሚናስ ሥጋ አንገታቸውን ዘረጉ ከቅዱስ ሚናስም ሥጋ እሳት ወጥታ እነዚያን አራዊት አቃጠለቻቸው ሰዎችም አይተው አደነቁ ደስታም አደረጉ ፈርተው ነበርና።

ወደ እስክንድርያ አገርም ደርሰው ሥራቸውን ፈጽመው ወደ ሀገራቸው በሚመለሱ ጊዜ የቅዱስ ሚናስን ሥጋ ከእሳቸው ጋር ሊወስዱ ወደው በገመል ላይ በጫኑት ጊዜ ገመሉ ከቦታው የማይነሣ ሆነ። ሁለተኛም በሌላ ገመል ጫኑት እርሱም መነሣትን እምቢ አለ። አብዝተውም ደበደቡት ገመሉም ከቶ አልተንቀሳቀሰም እነርሱም ያ ቦታ እግዚአብሔር የፈቀደለት መሆኑን አወቁ ቦታውንም አዘጋጅተው በዚያ ቀበሩት።

ጌታችንም በበግ እስከገለጠው ድረስ ብዙ ዘመናትን በዚያ ቦታ ኖረ ይህም ቤተ ክርስቲያኑ በከበረችበት በሰኔ ዐሥራ አምስት ቀን ተጽፎአል።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ቂርቆስ_ሰማዕት

ዳግመኛም በዚህች ዕለት ሕፃኑ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ልደቱ ነው። ቅዱስ ቂርቆስን አባቱ ቆዝሞስ እናቱ ኢየሉጣ ይባላሉ፡፡ በዚህች ቀን የተወለደ ሲሆን ሀገሩ በታችኛው እስያ ልዩ ስሙ ሀንጌቤን ይባላል፡፡ ሦስት ዓመት እንኳን ሳይሞላው በሁለት ዓመት ከዘጠኝ ወሩ ታላቅ ሰማዕትነትን ተቀብሏል።

ዘመኑ ዘመነ ሰማዕታት ኘበርና በዚያንም ወራት የክብር ባለቤት የሆነ ክርስቶስን በሚያምኑ የክርስቲያን ወገኖች ላይ ታላቅ መከራና ስደት ሆነ። ቅድስት ኢየሉጣም ከታናሽነቷ ጀምራ ደግ ናት። ስደትም እንደሆነ በሰማች ጊዜ መኰንኑን ከመፍራት የተነሣ ቅዱስ ቂርቆስን ይዛ ከሮም ከተማ ተሰዳ የኪልቅያ አውራጃ ከሆነ ከጠርሴስ ደርሳ ከዚያም በሀገሮች ውስጥ እየተዘዋወረች ተቀመጠች ።

ወደዚያች አገርም ያ ከእርሱ የሸሸችው መኰንን እለእስክንድሮስ መጣ ጭፍሮቹም ክርስቲያኖችን ፈለጓቸው። ይቺንም ቅድስት ኢየሉጣን አግኝተው ያዝዋትና ወደ መኰንኑ አደረሷት የክርስቲያን ወገንም እንደሆነች ነገሩት።

መኰንኑም "ሴትዮ ተናገሪ ከወዴት ሕዝብ ወገን ነሽ? ነገድሽ ምንድን ነው? ሀገርሽስ ወዴት ነው?" አላት ። የከበረች ኢየሉጣም እንዲህ ብላ መለሰችለት "የአንጌቤን ሰው ለሆንኩ ለእኔ ወገኖቼ ለኢቆንዮን አገር አለቆች የሆኑ ኤሳውሮሳውያን ናቸው። እኔም በአንተ ምክንያት ሸሽቼ ነበር እነሆ ዛሬ ግን በእጅህ ውስጥ ነኝ" አለችው።

መኰንኑም "በእጄ ውስጥ እንደተገኘሽ ታውቂያለሽን" አላት። "አሁንም የሚሻልሽን ምረጪ ስምሽንም ተናገሪ እኔንም እሺ በይኝና ለአማልክት ሠዊ" የከበረች ኢየሉጣም "ለረከሱ አማልክት እኔ አልሰዋም" አለችው። መኰንኑም "ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት። እርሷም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል ነው" አለችው። መኰንኑም "ይህስ ስንፍና ነው የሚጠቅምሽ አይደለም እንዳትሞቺ ስምሽን ስጪ ተናገሪ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "የኔ ስም ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞት የሚሽረው በሰዎች ዘንድ የምጠራበትን ከፈለግህ ስሜ ኢየሉጣ ነው" ብላ መለሰችለት።

መኰንኑም "ጽኑ የሆኑ ሥቃዮችን በላይሽ ሳይመጣ ተነሥተሽ መሥዋዕትን ለአማልክት አቅርቢ" አላት። የከበረች ኢየሉጣም "ዕውነት ነገርን ለመሥራት የምትሻ ከሆነ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነ ሕፃን ልጅ ይፈልጉ ዘንድ ወደ ሀገሩ መንደር ላክ ወዳንተም ያምጡትና የምንገዛለትንና የምናመልከውን እርሱ ይንገረን" አለችው።

ያን ጊዜም የሦስት ዓመት ልጅ ይፈልጉ ዘንድ መኰንኑ ወታደሮችን ላከ የሀገር ሰዎችም ልጆቻቸውን ሠውረዋልና አላገኙም ከዚያም ከከተማው ቅጽር ውጭ በፀሐይ መውጫ ወዳለው በረሀ በኩል ወጡ የቅድስት ኢየሉጣንም ልጅ አገኙት ይህ ሕፃን የስንት ዓመት ልጅ ነው ብለው ስለርሱ ጠየቁ ሰዎችም ይህ ሕፃን የሦስት ዓመት ሲሆን የክርስቲያናዊት መበለት ልጅ ነው አሏቸው።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Nov, 23:23


ያንንም ሕፃን ይዘው ወደ መኰንኑ ወሰዱት መኰንኑም መልኩ የሚያምርና ደም ግባት ያለው እንደሆነ በአየው ጊዜ "ደስ የምትል ደስተኛ ሕፃን ሰላምታ ይገባሃል" አለው። ሕፃኑም "እኔን ደስተኛ ማለትህ መልካም ተናገርክ፤ ላንተ ግን ደስታ የለህም እግዚአብሔር ለዝንጉዎች ደስታ የላቸውም ብሏልና።" ብሎ መለሰለት መኰንኑም ሕፃኑን "ሳልጠይቅህ ይህን ያህል ትመልስልኛለህን?" አለው። ሕፃኑም "ገና ከዚህ የሚበዛ ነገርን እመልስልሃለሁ" አለው።

መኰንኑም ሕፃኑን "ስምህ ማን ነው?" አለው። "ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ሕፃን ስሜ ክርስቲያን መባል ነው" ብሎ መለሰለት። መኰንኑም "ዳግመኛ እንዳትሞት ስምህን ንገረኝ" አለው። የከበረ ሕፃንም "ስሜ ክርስቲያን መባል እንደሆነ ነገርኩህ ሞክሼ ስም የምትሻ ከሆነ እናቴ የሰየመችኝ ቂርቆስ ነው።"

መኰንኑም ሕፃን ቂርቆስን "እሺ በለኝና ለአማልክት ሠዋ በሥጋህም ስታድግ እሾምሃለሁ በብዙ ወርቅና ብርም አከብርሃለሁ" አለው። ሕፃኑም "የሰይጣን መልእክተኛ ለዕውነትም ጠላቷ የሆንክ ከእኔ ራቅ" አለው።

መኰንኑም ሰምቶ ተቆጣ ደሙ እንደ ውኃ እስከሚፈስ ቆዳውን እንዲጨምቁትና እንዲገፉት አዘዘ። የከበረች ኢየሉጣም የልጅዋን ትዕግሥት ባየች ጊዜ እግዚአብሔርን አመሰገነችው።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ ጨውና ሰናፍጭ አምጡ አለ የሁለቱንም አፍንጮቻቸውን ከፍተው ያንን ጨውና ሰናፍጭ እንዲጨምሩባቸው አዘዘ ያን ጊዜ ሕፃኑ ትእዛዝህ ለጕረሮዬ ጣፋጭ ሆነ ከማርና ከስኳርም ለአፌ ጣመኝ ብሎ ጮኸ።

ሁለተኛም መኰንኑ እንዲህ ብሎ አዘዘ የረዘሙና የተሳሉ በእሳትም እንደ ፍም የጋሉ ዐሥራ አራት የብረት ችንካሮች አምጡ ሰባቱን በእናቱ አካላት ውስጥ ጨምሩ በሕፃኑም ሁለት በጆሮዎቹ ሁለት በዐይኖቹ ሁለት በአፉና በአፍንጫው አንድ በልቡ ጨምሩ እንዲህ ሲጨመርበት ጆሮዎቹ እንዲያኖሩ ዐይኖቹም ይጠፉ ዘንድ አንደበቱም ይቃጠል ዘንድ ወደ ልቡም ጽኑ ሕማም ገብቶ እርሱ ከዚህ ዓለም በሞት እንዲለይ ለእናቱም እንዲሁ አድርጉ። ችንካሮችም በቅዱሳኑ በሥጋቸው ሁሉ ተጨመሩ።

የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ትእዛዝ የብረቶቹ ግለት ጠፍቶ እንደ በረዶ ቀዘቀዘ ጤነኞችም ሆኑ መኰንኑም ወደ ወህኒ ወስዳችሁ በዚያ አሥራችሁ ዝጉባቸው አለ።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ የሥቃይ መሣሪያ ይሠራ ዘንድ አንዳዝዘው ብረትን የሚያቀልጥ ሰው አምጡልኝ አለ። በአመጡለትም ጊዜ ሰይጣኑ ወደ መኰንኑ ልብ ገብቶ አንደበቱን ዘጋውና መናገር ተሳነው ሕፃኑ ፈጥኖ አክሊልን ለመቀበል እንደሚተጋ ሰይጣን ስለ አወቀ ስለዚህ ዘጋው።

ከዚህም በኋላ ሕፃኑ ሠራተኛውን ጠርቶ እኔንና እናቴን የሚያሠቃዩበትን የሥቃይ መሣሪያ መሥራት ትችላለህን ይህ መኰንን ግን ምንም የሚያውቀው ነገር የለም አለው ሠራተኛውም እንደምትሻው በል ንገረኝ እንደምታዝዘኝ እኔ መሥራት እችላለሁ አለው።

ሕፃን ቂርቆስም ሊአዝዝ ጀመረ እንዲህም አለ ሁለት መላጫዎች ስፋታቸው አራት ክንድ የሆነ ለእኔና ለእናቴ ሥራ። ዳግመኛም የሚያስጨንቅ ራስን የሚመታና የሚሰብር አንገትንም የሚያሥር የሚዝቅም ሹካ ዐይንንም የሚያወልቅ አካልንም የሚበሳሳ አፍንጫንም የሚያጣምምና የሚሰብር ጆሮንም የሚልጥ ሕዋሳትን የሚፈታና የሚለያይ እንደ ልጓም ሁኖ ምላስን የሚቆርጥ በሰውነትም ውስጥ ገብቶ የሚንቀሳቀስ ቆላፋ ጉጠትን ጐኖችንም የሚፍቅና የሚቆለምም አስጨናቂ የሆነ ጉልበቶችንና ጭኖችን የሚሰብር ጅማቶችንም የሚቆራርጥ ሥሮችንም የሚመዝ በዚችም አስጨናቂ መሣሪያ ጅማቶችን የሚታታ አድርግ።

ዳግመኛም በላም አምሳል ሰፊ መቀመጫ ከናስ ሥራ ሦስት ቀዳዳዎችንም በዚያ መቀመጫ ውስጥ ቅደድ። በቁመቴም ልክ ሦስት ችንካሮችን ሥራ የችንካሮቹንም ራስ ከናስ አድርገህ በውስጡ ከሚጠሩት ዘንድ ፈጽሞ የማይለይ ልዩ ሦስት ብለህ ጻፍ።

ዳግመኛም ጠምዝዞ ወደ ላይ የሚያወጣ ሁለት መሣሪያ ሁለት መጋዞችን ሁለት የብረት ምጣዶችን ሥራ አሁንም አንድ ታላቅ ጋን ሠርተህ በውስጡ አንገትን የሚጠመዝዝና የሚሠነጥቅ ተሽከርካሪ መሣሪያ አድርግ።

በውስጥ የተሸሸገ የሆድ ዕቃን የሚመረምር እጅን ከብረት ሥራ እኔ የጻዕር ስቃይን የምሠቃይበት ይህ ነው አለ። ብረት ሠሪውም ሰምቶ እጅግ አደነቀ የሚረዱትንም ከሀገር ውስጥ መቶ ሠራተኞችን ሰብስቦ መሥራት ጀመረ በአርባ ቀንም ጨረሰ።

ከዚህም በኋላ መኰንኑ እለእስክንድሮስ ቂርቆስንና እናቱን ወደ አደባባይ ያመጡአቸው ዘንድ አዘዘ ያን ጊዜ አንደበቱ ተፈትቶ ነበርና እንዲህም አለ ሕፃኑንና እናቱን ከቆዳቸው ጋር ራሳቸውን ላጩአቸውና በላያቸው የእሳት ፍሞችን ጨምሩ እርር ብለው እንዲቃጠሉ ዳግመኛም አራት ችንካሮችን ከትከሻዎቹ እስከ ተረከዙ ድረስ እንዲተክሉበት አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ መጥቶ ሥቃዮችን ከርሱ አራቀ።

ዳግመኛም ከጥዋት እስከ ማታ ከሥቃይ መሣሪያዎች ውስጥ ጨምረው አዋሏቸው ግን ማሠቃየት ተሳናቸው። ከዚህም በኋላ ከማምጠቂያው ውስጥ ጨምረው መገዙአቸውና አመድ እስከሆኑ ከቅባትና ከጨው ጋር በብረት ምጣድ ውስጥ ቆሉአቸው ጌታችንም ከሞት አስነሥቶ አዳናቸው።

ወደ መኰንኑም በገቡ ጊዜ እንዲህ አላቸው በእውነት ከሙታን ተለይታችሁ የተነሣችሁ ከሆነ ይህ ጫማዬ ከእግሬ ወጥቶ እንደ ቀድሞው ሕያው እንዲሆን አድርጉ ሕፃን ቂርቆስም በጸለየ ጊዜ ያ ጫማ ታለቅ በሬ ሆነ ከአንገቱም ፍየል ወጣ።

በዚያንም ሰዓት ለዐሣራ አንድ ሽህ አራት ሰዎች በሬውንና ፍየሉን አርደው ምሳ እንዲአደርጉላቸው መኰንኑ አዘዘ እንዲህም አለ ይህ በቅቷቸው ከጠገቡ ከዚህም ሌላ ምግብ ካልፈለጉ የተሠራው ሁሉ ዕውነተኛ ነዋሪ ነው። ከዚህም በኋላ አርደው ምሳ አደረጉላቸውና ከፍየሉ ሥጋ ስድስት እንቅብ ከበሬው ሥጋ አራት እንቅብ አተረፉ መኰንኑም የተረፈውን ሥጋ አይቶ ወደ ባሕር እንዲጥሉት አዘዘ።

መኰንኑም ቢያፍር የሕፃኑን ምላስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ምላሱን መለሰለት። ዳግመኛም በታላቅ ጋን ውኃ እፍልተው ሕፃን ቂርቆስንና እናቱን ኢየሉጣን ይጨምሩአቸው ዘንድ አዘዘ። እናቱም አይታ ፈራች። ልጅዋም ወደ እግዚአብሔር በጸለየላት ጊዜ አምላካዊ ኃይልን አሳደረባትና ከልጅዋ ጋር ወደ ጋኑ ገባች። እንደ ውርጭም ቀዝቀዛ ሆነ ደግሞም በውስጡ መንኰራኲር ወዳለበት የብረት ምጣድ እንዲጨምሯቸውና ሥጋቸው እሰከሚቦጫጨቅ እንዲስቡአቸው አዘዘ የእግዚአብሔርም መልአክ በሕይወት አወጣቸው።

መኰንኑም እነርሱን ማሸነፍ በተሳነው ጌዜ ቸብቸቧቸውን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ። በዚያን ጊዜ ለስም አጠራሩ ስግደት የሚገባው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ሕፃን ቂርቆስንም የምትሻውን ለምነኝ አለው።

ሕፃኑም ሥጋዬ በምድር አይቀበር ስሜን ለሚጠራ መታሰቢያዬን ለሚያደርግ ቤተ ክርስቲያኔን ለሚሠራ የተጋድሎዬን መጽሐፍ ለሚጽፍና ለሚያጽፍ ወይም ለሚያነበው ለቤተ ክርስቲያኔ መባ ለሚያገባ በውስጧም ለሚጸልይ ለሁሉም ፍላጎታቸውን ስጣቸው። ኃጢአታቸውንም ይቅር በል ስሜም በሚጠራበት በዚያች ቦታ የከብት ዕልቂት አይምጣ፤ በሰውም ላይ እባር ቸነፈር በእህልም ላይ ድርቅ የውኃም ማነስ አይሁን።

መድኃኒታችንም የለመንከኝን ሁሉ እሰጥሃለሁ አንተም በቀኜ ትኖራለህ ሥጋህንም ኤልያስ በዐረገበት ሠረገላ ውስጥ አኖራለሁ አለው። ሕፃን ቂርቆስም በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ ብሎት ጌታችንን አመሰገነው። ከዚህም በኋላ በሌሊቱ እኩሌታም ከእናቱ ጋር አንገቱን ተቆረጠ መድኃኒታችንም በማይጠፋ አክሊል ጋረደው ነፍሶቻቸውንም በታላቅ ክብር ከእርሱ ጋር አሳደገ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Nov, 19:50


💕ከዘማሪያን የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይ ፈ ል ጋ ሉ ? 🔔 💕

[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
[┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪ አቤል መክብብ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕ዘማሪ ዲያቆን ሙሉቀን ከበደ💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ቀሲስ ምንዳዬ ብርሃኑ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛
┏•••••••••••••••••••••••••••••••┓
💕 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ 💕
┗•••••••••••••••••••••••••••••••┛

🌷👥 የሁሉንም ዘማሪያን መዝሙር ለማግኘት 🔔 👇
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Nov, 19:10


በግምት ከሌሊቱ 8 ሰአት ገደማ ነው ሶስት ጓደኛማቾች እንደ ለመደባቸው ቅዳሜን ወጥተው ክለብ ለክለብ እየተዝናኑ ሰአታትን አስቆጥረዋል እንደ አጋጣሚ ሆኖ እጃቸው ላይ ያለውን ብር የትራንስፖርት እንኳን ሳያስከሩ መጨረሳቸውን ያስተዋሉት ከረፈደ ነበር ያው የሁልጊዜ ቤታችን ስለሆነ ዱቤ ይሠጡናል ብለው አስተናጋጁን ይጠሩትና የተፈጠረውን ያስረዱታል እንደ አጋጣሚ ሆኖ ሞባይል ባንኪንግ የማይጠቀሙበትን ተቀያሪ ስልካቸውን እንደያዙና እጃቸው ላይ በዚህ ሰአት ምንም ብር እንደሌላቸው ይነግሩታል እሱም ወደ ማናጀሩ መሄድ ሲጀምር.....see more

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Nov, 16:09


በአገልግሎታችሁ ምንም ፈተና ካልገጠማችሁ!
ሰይጣን ንቋችኋል ማለት ነው

ዲ/ን ሄኖክ ሀይሌ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Nov, 08:53


ዕቅበተ እምነት



👉ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ
👉ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ
👉በርእሰሊቃዉንት አባ ገብረኪዳንግርማ





በቸር ዋሉ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

11 Nov, 21:03


ዘገብረ ተአምር›› በሚባል ቦታ አሁንም ድረስ ቆሞ ይታያል፡፡

ጻድቁ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ በ1312 ዓ.ም የመሠረቱት ገዳማቸው ደብረ በንኮል ከአክሱም በእግር ሦስት ሰዓት ያስኬዳል፡፡ ይኸውም በንግሥተ ሳባ ቤተ መንግሥት አድርጎ የቀዳማዊ ሚኒሊክን መቃነ መቃብር አልፎ በመሄድ ነው፡፡ ወይም በመኪና ለመጓዝ አክሱም ጉበዱራን አቋርጦ ውቅሮ ማራይ ከተማን አልፎ በስተ ሰሜን አቅጣጫ 10 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ በስተ ምዕራብ የአቡነ አላኒቆስ ዘማይበራዝዮን ገዳም፣ በስተ ምሥራቅ የአቡነ ሰላማን ገዳም እየተለመከቱ እንደተጓዙ ጥቅጥቅ ባለ ደን የተሸፈነውን ደብረ በንኮልን ያገኙታል፡፡ ኅዳር 20 ጻድቁ ስለሚነግሱ ገዳሙም ለአክሱም ቅርብ ስለሆነ ይህ ለአክሱም ጽዮን ተጓዦች ተጨማሪ ትልቅ በረከት ነው፡፡

ደብረ በንኮል ማለት ‹‹ሙራደ ቃል›› ማለት ነው፡፡ ትርጉሙም የምሥጢር መውረጃ ማለት ነው፡፡ በቦታው ላይ ሱባኤ ለያዘ ሰው እንደ ቅዱስ ያሬድና እንደ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ምሥጢር እንደሚገለጥለት የሚጠቁም ነው፡፡ በ14ኛው መ/ክ/ዘ የነበሩት ደጋግ መነኮሳት ሕይወታቸውን በሙሉ በምንኩስና፣ በጸሎትና በታላቅ ተጋድሎ መኖር ሲፈልጉ ከደብረ ዳሞ፣ ከሐይቅ እስጢፋኖስ፣ ከደብረ ሊባኖስና ከሌሎቹም የሀገራችን ክፍሎች እየተነሡ ወደ ደብረ በንኮል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ነበር የሚሄዱት፡፡

የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ቃልኪዳን፡- ጻድቁ ባርከው ያፈለቁት ጸበላቸው ላበደ ሰው መድኃኒት ነው፡፡ ከመቃብራቸው ላይ የሚነሣውን አፈር ጻድቁ ባርከው ባፈለቁት ጸበላቸው ታሽቶ በእጃቸው መስቀል ተባርኮና ታሽቶ የሚዘጋቸውን የአቡነ መድኃኒነ እግዚእን እምነታቸውን በእምነት ሆኖ የያዘን ሰው ንብረቱን ሌባ ቀማኛ ዘራፊ አይሰርቀውም፤ የመኪና አደጋ አይደርስበትም፤ ጥይት አይመታውም፡፡ ‹‹በእምነት ሆኖ የያዘን ሰው›› መባሉን ልብ ይሏል፡፡ ይኸውም ለጻድቁ የተሰጣቸው ታላቅ ቃልኪዳን ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ፍሬ_ካህን

ዳግመኛም በዚህች ቀን አቡነ ፍሬ ካህን አረፉ።
ጻድቁን በመጀመሪያ ከጎጃም ተነሥተው በታዘዘ መልአክ መሪነት ትግራይ ደብረ በንኮል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ገዳም ሄደው መንነው መነኮሱ፡፡ ጻድቁ ስድስት ክንፍ የተሰጣቸው ሲሆኑ በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎ ይታወቃሉ፡፡ አቡነ ፍሬ ካህን ወንጌልን ሲሰብኩ ሙታንን እያስነሡ በሲኦል ውስጥ ስላለው መከራና ሥቃይ እንዲመሰክሩ ያደርጓቸው ነበር፡፡ ጻድቁ ሐይዳ ገዳም ታቦት ተቀርጾላቸው ገድል የተጻፈላቸው ቢሆንም ሙሉ ገድላቸው ታትሞ ለምእመኑ አልተዳረሰም፡፡ አቡነ ቶማስ ካረፉ በኋላ አቡነ ፍሬ ካህን ገዳማቸውን ተረክበው በጽድቅ መንገድ መነኮሳቱን አስተዳድረዋል፡፡

አቡነ ፍሬ ካህን አፈር ከኢየሩሳሌም አምጥተው ዋልድባ ሲደርሱ መነኮሳቱ "ገዳሙን በአህያ አታስረግጥ" ቢሏቸው አህዮቹን ክንፍ አውጥተው እንዲበሩ አድርገዋቸዋል፡፡

አባታችን ሽሬ ደብረ ሐይዳ አቡነ ፍሬ ካህን የተባለ ትልቅ ገዳም አላቸው፡፡ ገዳሙ ከአቡነ ቶማስ ዘሐይዳ ገዳም ጋር አንድ ነው፡፡ ወደዚህ ገዳም ውስጥ ሥጋና ቅቤ ተበልቶም ሆነ ተይዞ መውጣት ፈጽሞ አይቻልም፡፡ አልታየሁም ተብሎ በድብቅ ሥጋ ተይዞ ቢገባ ሥጋው ይተላል፡፡ ሥጋና ቅቤ የበላ ሰውም ዕለቱን በድፍረት ወደ ገዳሙ ቢገባ ሆዱ በኃይል ይነፋል በዚህም ይታወቅበታል፡፡ ከብቶችም ቢሆኑ ወደ ገዳሙ አይወጡም፣ ማንም ሳይመልሳቸው ራሳቸው ይመለሳሉ፡፡ የአቡነ ፍሬ ካህን ዕረፍታቸው ኅዳር 3 ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባት_ኪርያቆስ

በዚህች ቀን ከቆሮንቶስ አገር ቅዱስ አባት ኪርያቆስ አረፈ።

የዚህም አባት ወላጆቹ ሃይማኖታቸው የቀና የከበሩ ናቸው የቤተክርስቲያንን ትምህርትና የቀናች ሃይማኖትን አስተማሩት ከዚህም በኋላ የቆሮንቶስ አገር ኤጲስቆጶስ ወደ ሆነ ወደ አባ ጴጥሮስ አቀረቡት እርሱም በላዩ ጸልዮ አናጒንስጢስነት ሾመው ለአባ ጴጥሮስም የወንድሙ ልጅ ነው።

ከዚህም በኋላ ዘወትር መጻሕፍትን የሚያነብ የቃላቸውንም ትርጓሜ የሚመረምር የቤተ ክርስቲያንንም ሥርዓቷንና ሕጓን የሚያጸና ሆነ በትምህርቱና በእውቀቱም ከብዙዎች ከፍ ከፍ አለ ኤጲስቆጶሱም መጻሕፍት ማንበብን እንዳያቋርጥ ያዝዘው ነበር እርሱም ለሕዝቡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለኤጲስቆጶሱም በቤቱ ያነብለት ነበር። መጻሕፍትንም በሚያነብለት ጊዜ ኤጲስቆጶሱ በእርሱ ደስ ይለው ነበርና።

ዕድሜውም ዐሥራ ስምንት ዓመት በሆነ ጊዜ ሚስትን ያጩለት ዘንድ ወላጆቹ ጠየቁት እርሱ ግን ይህን አልወደደም ግን ከገዳማት ወዳንዱ ይሔድ ዘንድ እንዲአሰናብቱት ወላጆቹን ለመናቸው ከዚያም በኋላ አዘውትሮ ወደ ገዳማት የሚሄድና ወደ ወላጆቹ የሚመለስ ሆነ። መመላለሱም ከበዛ ዘንድ የከበረች የምንኲስናን ልብስ ሊለብስ ወዶ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ከኢየሩሳሌሙ ኤጲስቆጶስ ከአባ ቄርሎስ ጋር ተገናኝቶ ስለ ምንኲስና ኀሳቡን ሁሉ ነገረው። እርሱም በጎ ሥራን ወደሃል አለው ታላቅ አባትም እንደሚሆንና በእርሱም የብዙዎች ነፍሳት ብሩሃን እንደሚሆኑ ትንቢት ተናገረለት።

ከዚህም በኋላ የመነኰሳት አባት ወደ ሆነ በፍልስጥዔም ወደ ሚኖር ወደ ክቡር አባ ሮማኖስ ላከው እርሱም በደስታ ተቀብሎ የምንኵስናን ልብስ አለበሰው። የምንኵስናንም ሥርዓት ያስተምረው ዘንድ የሰይጣንንም ተንኮል ያስረዳው ዘንድ በዚያው ገዳም ለሚኖር አንድ አረጋዊ ሰጠው። ከዚህም በኋላ በጾም በጸሎት በስግደት በመትጋት በታላቅ ድካም በቀንና በሌሊት በገድል ተጸምዶ በትዕግሥት በትሕትና በቅንነት ኖረ።

እግዚአብሔርም የመፈወስን ሀብት ሰጥቶት ወደርሱ የሚመጡትን በሽተኞች ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ የትሩፋቱና የቅድስናውም ዜና በሁሉ ቦታ ተሰማ ። የኢየሩሳሌሙ ኤጲስቆጶስ አባ ቄርሎስም የክብር ባለቤት የሆነ መንፈስ ቅዱስን ስለ አቃለለ መቅዶንዮስ መቶ ሃምሳው ኤጲስቆጶሳት አንድነት ወደሚሰበሰቡበት ወደ ቊስጥንጥንያ በሚሔድ ጊዜ ይህን አባት ኪርያቆስን አባ ቄርሎስ ከእርሱ ጋር ወሰደው በላያቸው በአደረ መንፈስ ቅዱስ ስም ተከራክረው ከሀዲ መቅዶንዮስን ረቱት ከምእመናንም ለይተው አሳደዱት።

ከዚህም በኋላ በመልካም ሽምግልና እግዚአብሔርን አገልግሎ በሰላም አረፈ። ከዕረፍቱም በኋላ እግዚአብሔር ድንቆች የሆኑ ብዙ ተአምራትን ከሥጋው ገለጠ ከእርሳቸውም አንዱ ከኢየሩሳሌም ገዳማት በአንዱ ሥጋው ይኖራል። ከአረፈበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ዛሬ ሥጋው አልተለወጠም ወደ ኢየሩሳሌም የሚሔዱ ሁሉ ያዩታል እነርሱም በቅርብ ጊዜ እንዳረፈ ያስባሉ እርሱ ግን ያረፈው ለአኖሬዎስና ለአርቃዴዎስ አባታቸው በሆነ በታላቁ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ዘመን ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_አትናቴዎስና_እኅቱ_ኢራኢ

በዚችም ቀን አባ አትናቴዎስና እኅቱ ኢራኢ አረፉ። እሊህንም ቅዱሳን ከሀዲ ንጉሥ መክስምያኖስ ጽኑዕ የሆነ ሥቃይን አሠቃያቸው።

በማሠቃየትም በደከመ ጊዜ ዕራቁታቸውን ከጉድጓድ ጨመራቸው በላያቸውም የጒድጓዱን አፍ ዘጋ በውስጧም ነፍሳቸውን አሳለፉ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበሉ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዓምደ_ሚካኤል

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

11 Nov, 21:03


#ኅዳር_3

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
#የአቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ - እረፍት
#የአቡነ_ፍሬ_ካህን - እረፍት
#የቅዱስ_ኪርያቆስ - እረፍት
#የአባ_አትናቴዎስና_እኅቱ_ኢራኢ - እረፍታቸው
#የቅዱስ_ዓምደ_ሚካኤል - እረፍት ቀን ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_መድኃኒነ_እግዚእ_ዘደብረ_በንኮል

ኅዳር ሦስት በዚህች ቀን አቡነ መድኃኒነ እግዚእ አረፉ።
ከደጋግ ክርስቲያኖች ከቀሲስ ሰንበት ተስፋነ እና ከኅሪተ ማርያም በ1180 ዓ.ም በሥዕለት የተወለዱት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅግ አስደናቂ ገድልና ትሩፋት ያላቸው ጻድቅ ቢሆኑም ብዙው ሕዝበ ክርስቲያን እንደሚገባቸው መጠን ያላወቃቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ መዘንጋታቸው እጅግ ከሚያስቆጩን አባቶች መካከል ትልቁን ድርሻ የሚወስዱት የደብረ በንኮሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ እስቲ ቀጥሎ ስማቸውን የጠቀስኳቸውን እነዚህን ቅዱሳን አባቶች ታሪካቸውንና የጽድቅ ሕይወታቸውን አስታውሱት፡- እነርሱም አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ፣ አቡነ ያሳይ ዘማንዳባ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘቆየፃ፣ አቡነ ሳሙኤል ዘጣሬጣ፣ አቡነ ታዴዎስ ዘባልታርዋ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ ዘጉጉቤ እና አቡነ ዮሐንስ ዘጉራንቄ እነዚህን የመላእክትን ሕይወት በምድር የኖሩ ታላላቅ የሀገራችንን ቅዱሳን አስተምረውና አመንኩሰው ለጽድቅ ያበቋቸው አባት አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡

አቡነ መድኃኒነ እግዚእ እነዚህን ሰባቱን ቅዱሳን በአንድ ጊዜ ሲያመነኩሷቸው በዚያው ቅጽበት መንፈስ ቅዱስ ወርዶ ገዳሙን ደብረ በንኮልን በብርሃን አጥለቅልቆት ታይቷል፡፡ ከሰማይም የምስክርነት ድምፅ ተሰምቷል፡፡ በዚህም ምክንያት አንድ ላይ የመነኮሱት እነዚህ ሰባቱ ቅዱሳን ‹‹ሰባቱ ከዋክብት›› እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ እነዚህም ሰባቱ ከዋክብት የጣናን ባሕር በእግራቸው ጠቅጥቀው ተሻግረው ብዙዎቹን ደሴቱ ላይ ያሉ አስደናቂ የጣና ገዳማትን የመሠረቱት ናቸው፡፡ ከእነርሱም ውስጥ ትልቅ ጠፍጣፋ ድንጋይን እንደጀልባ ተጠቅመው በእርሱ ላይ ሆነው ወደ ደሴት የገቡ አሉ፡፡ በእግራቸውም እየረገጡ ባሕሩን የተሻገሩ አሉ፡፡ በሌላም ቦታ በየብስ የተሰማሩትም ቢሆኑ መጻሕፍቶቻቸውን በአንበሳ ጭነው የተጓዙ አሉ፡፡ በደብረ ሊባኖሱ ሐዲስ ሐዋርያ የኢትዮጵያ ብርሃኗ በሆኑት በአቡነ ተክለ ሃይማኖት እጅ ከመነኮሱ በኋላ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም በተራቸው ያስተማሯቸውና ያመነኮሷቸው መነኮሳት ቁጥራቸው በውል አይታወቅም፡፡ አቡነ ተክለ ሃይማኖትም ለአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ‹‹ስፍር ቁጥር የሌላቸው ከዋክብት ቅዱሳንን›› በመንፈስ ቅዱስ እንደሚወልዱ ትንቢት ተናግረውላቸው ነበር፡፡ የተንቤኑን አቡነ ዐቢየ እግዚእን፣ የዞዝ አምባውን አቡነ አብሳዲን ጨምሮ አባታችን መድኃኒነ እግዚእ ብርሃን ሆነው በጣም ብዙ ቅዱሳንን የለኮሱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ‹‹ወላዴ አእላፍ ቅዱሳን›› ይባላሉ፡፡

የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ልጆች ዛሬ ግሸን ላይ በክብር ተቀምጦ ሀገራችንን ከመዓት እየጠበቀ ያለውን የጌታችንን ቅዱስ መስቀል ያመጡትም እነርሱ ናቸው፡፡ ዐፄ ዳዊት በዘመናቸው ረኃብ ስለነተሳ የደብረ ቢዘኑን አቡነ ፊሊጶስን ከገዳማቸው አስጠርተው ‹‹ምን ባደርግ ይሻለኛል?›› ብለው አማከሯቸው፡፡ አቡነ ፊሊጶስም ‹‹የጌታችንን መስቀል ያስመጡ›› ብለው መከሯቸው፡፡ ንጉሡ ዐፄ ዳዊትም ከኢየሩሳሌም፣ ከቍስጥንጥንያና ከእስክንድርያ መንግሥታት ጋር ተጻጽፈው ዓሥሩን ታላላቅ ቅዱሳን መርጠው ይዘው ሄደው መስቀሉን መስከረም 10 ቀን አምጥተውታል፡፡ በጽድቅ ሥራቸውና ተአምራትን በማድረግ በወቅቱ ታዋቂ የነበሩትና ቅዱስ መስቀሉን ያመጡት ዐሥሩ ቅዱሳንም የደብረ ቢዘኑ አቡነ ፊሊጶስ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ ኂሩተ አምላክ፣ የጣና ደሴቱ አቡነ እንድርያስ፣ አቡነ በትረ ማርያም፣ አቡነ ዮሐንስ፣ አቡነ ታዴዎስ፣ አቡነ ያፍቅረነ እግዚእ፣ አቡነ ዘካርያስ፣ አቡነ ያሳይና አቡነ ቶማስ ናቸው፡፡

የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ተአምራታቸው እጅግ ብዙ ነው፡፡ አራዊት ሁሉ እንደሰው ያገለግሏቸው የነበር፡፡ ውኃ የሚያመላልስላቸውንና የሚያገለግላቸውን አህያ አንበሳ ቢበላባቸው በአህያው ምትክ አንበሳውን ድፍን 7 ዓመት ለገዳማቸው ውኃ አስቀድተውታል፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡- ለአባታችን ውኃ የሚያመላልስላቸውና የሚያገለግላቸው አንድ አህያ ነበራቸው፡፡ ውኃው የሚገኘው እርሳቸው ካሉበት በጣም እርቆ በእግር የ3 ሰዓት መንገድ ከተሄደ በኋላ ነው፡፡ ነገር ግን አህያቸው እንደ ሰው እየተላላካቸው ይቀዳላቸው ነበር፡፡ አንድ ግን ከመንገድ አንበሳ አግኝቶት ግማሽ አካሉን በልቶት ሄደ፡፡ አባታችንም የአህያቸውን ተረፈ በድን አግኝተው በማዘን ‹‹ውኃ የሚያመላልስልኝ ረዳቴ ይህ አህያ ብቻ ነበር፣ አሁንም አህያዬን የበላህ አውሬ እንድታነጋግረኝ እፈልጋለሁ›› ቢሉ በአንበሳ ተበልቶ የሞተው የአህያው ግማሽ አካል አፍ አውጥቶ አንድ አንበሳ እንደበላው ነገራቸው፡፡ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም በዚህ እጅግ ደስ ተሰኝተው ፈጣሪያቸውን ካመሰገኑ በኋላ አህያቸውን የበላውን አንበሳ ከጫካው ውስጥ ጮኸው ጠሩት፡፡ አንበሳውም ከሌሎቹ አንበሳ ተለይቶ ወደ እርሳቸው በመምጣት እግራቸው ሥር ወድቆ ሰገደ፡፡ አባታችንም ‹‹አህያዬን የበላኸው አንተ ነህን?›› ብለው ሲጠይቁት አንበሳውም በሰው አንደበት ‹‹አዎ እኔ ነኝ›› አላቸው፡፡ እርሳቸውም ፈጣሪያቸውን በድጋሚ ካመሰገኑ በኋላ አንበሳውን ‹‹በል ና ተከተለኝ በአህያዬ ምትክ ታገለግለኛለህ›› አሉት፡፡ አንበሳውም ተከትሏቸው ወደ በዓታቸው በመግባት ለ7 ዓመታት እንደ አህያቸው ውኃ እየቀዳ አገልግሏቸዋል፡፡ የአንበሳው ቆዳ ዛሬም በገዳማቸው ደብረ በንኮል በክብር ተቀምጠቷል፡፡

አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባንም አመንኩሰው መርቀው ሲሸኟቸው እንዲያገለግሏቸው አንበሶችን ከጫካ ጠርተው ያዘዙላቸው አባታቸው አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ናቸው፡፡ የዋልድባው አቡነ ሳሙኤል አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ከመነኮሱ በኋላ በደብረ በንኮል 12 ዓመት አባታችንን ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ እሳት እስከማያቃጥላቸው ድረስ ከብቃት ደረጃ ላይ ሲደርሱ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ መርቀው በማሰናበት በዓት እንዲያጸኑ ሲያደርጓቸው አቡነ ሳሙኤል በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ጣና ደሴት ገብተው ሱባኤ ያዙ፡፡ በዚያም ሳሉ አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ማረፋቸውን በመንፈስ ዐውቀው ሲያለቅሱ ጌታችን የአቡነ መድኃኒነ እግዚእን ነፍስ በእቅፉ አድርጎ ወደ ገነት ሲያሳርጋት አሳያቸው፡፡ ወዲያውም ጌታችን በብርሃን ሰረገላ አድርጎ አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባን ደብረ በንኮል አድርሷቸዋል፡፡ በዚያም እስከ 40ኛው ቀን ከቆዩ በኋላ በዚሁ ዕለት ሲቀድሱ ክንድ ከስንዝር ከመሬት ከፍ ብለው ቅዱሳን ሐዋርያት እየተራዱዋቸው ከቀደሱ በኋላ ወደነበሩበት መልሷቸዋል፡፡ የጻዲቁ የአቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዕረፍታቸው ኅዳር 3 ቀን 1360 ዓ.ም ሲሆን ጠቅላላ ዕድሙያቸውም 180 ዓመት ነው፡፡

ዐፄ ፋሲል ጻድቁ የተከሏቸውን የጥድ ዛፎች በሙሉ ተቆርጠው የአክሱም ቤ/ክ እንዲሠራበት አዋጅ አወጁና መልእክተኞች መጥተው ዛፎቹን ሲቆርጡ መነኮሳቱ ግን ‹‹ጻድቁ አባታችን የተከሏቸው የጥድ ዛፎች መቆረጥ የለባቸውም›› ብለው ቢከራከሩም ሰሚ አላገኙም፡፡ መነኮሳቱም ወደ እግዚአብሔር ቢያመለክቱ ጩኸታቸው ተሰምቶላቸው ወዲያው እየተቆረጡ ያሉት የጥድ ዛፎች በሙሉ በተአምራት ወደ ወይራ ዛፍነት ተለወጡ፡፡ የወይራ ዛፎቹም ለዐፀድ እንጂ ለሕንፃ የማይመቹ ጎባጣ ሆኑ፡፡ የዚህም ምልክቱ ዛሬም ድረስ አለ፡፡ ግንዱ ጥድ ዛፉ ግን ወይራ የሆነ ትልቅ ዛፍ ‹‹ወይራ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

11 Nov, 19:08


🧕👉🏾 ሴት በወር አበባዋ ጊዜ መጸለይ ትችላለች⁉️
👉🏾 ግለ አውናን / ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ማግባት ይችላልን
👉🏾 በሱባኤ ወቅት ህልመ ሌሊት (ዝንየት) ቢመታን ምን እናደርጋለን
👉🏾 ሕልመ ሌሊት በራሱ ኃጢአት ነውን‼️
👉🏾 ሕልመ ሌሊት በምን ይከሰታል
👉🏾 ከዝሙት አጋንንት እና ከዝንየት በተጨማሪ በሕልመ ሌሊት የሚፈትነን አጋንንት የትኛው ነው
👉🏾 የሕልመ ሌሊት መፍትሔ ምንድን ነው⁉️
👉🏾 ቁርባን ቆርበን ሕልመ ሌሊት እንዳይጸናወተን ምን ማድረግ አለብን⁉️❤️በማርያም ይህን ቻናል ይቀላቀሉ❤️
            👇👇👇
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

         ◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
         █   𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲      █          
         ◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
      
         👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
         የይቱብ ቻናላችን
         👇👇👇
             🔔
     🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺‌‌

🤗ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🤗
❤️ፊላታዎስ ሚዲያ❤️
👳🏽‍♂ በግሩም እና በተወዳጅ ዘማሪያን ይቀርባል ከታች
ባለው ሊንክ ሰብስክራቭ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።
         👇🏽👇🏽

https://youtu.be/PYhgHxupzLI?si=pQaqogjyjDUcNXW

https://youtu.be/PYhgHxupzLI?si=pQaqogjyjDUcNXW

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

11 Nov, 18:34


⛪️📚🙏
1, እመጓ
2, ዝጎራ
3, መርበብት
4, ዴርቶጋዳ
5, ዮራቶራድ
6, ዣንቶዣራ
7,መጽሐፈ ሄኖክ
8, ቤተክርስቲያንህን እወቅ እንዳትሆን መናፍቅ
9, ፍኖተ አእምሮ
9, አዳም እና ጥበቡ
10, ዝክረ መስቀል
11, ሰይፈ ሥላሴ
12, ፍትሐ ነገስት
13, መጽሐፈ መነኮሳት
14, ከአክራሪ እስልምና ወደ ክርስትና
16, ህግጋተ ወንጌል
17, ነገረ ማርያም በጥንታዊቷ ቤተከርስቲያን
18, ድርሳነ ሚካኤል ወ ገብርኤል
19, ውዳሴ ማርያም በግእዝ
20, ግድለ ተክለሃይማኖት
21, ገድለ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሰጫ
22, የወጣቶች ህይወት
23, መጽሐፈ ገድለ ሐዋርያት
24, ኦርቶዶክስ መልስ አላት
25, የዋልድባ ገዳም ታሪክ

📚📚የቱን ኦርቶዶክሳዊ መፅሀፍ ማንበብ ይፈልጋሉ የሚፈልጉትን መፅሀፍ በመንካት ያንብቡ መልካም ንባብ📖

    
                      ይቀላቀሉን                   

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

11 Nov, 12:36


ሥራ ሰለሌለኝ እጮኛዬን ላጣት ነው

በአቤል ተፈራ በላይ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

11 Nov, 07:53


ምክረ አበዉ


መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ በአባቶች

በማስተዋል እናዳምጥ

በቸር ዋሉ💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

11 Nov, 03:27


#የማለዳ የሕይወት ቃል
         

መዝሙር 103፥ 10-13

እንደ ኃጢአታችን አላደረገብንም፥
እንደ በደላችንም አልከፈለንም።
ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል፥
እንዲሁ እግዚአብሔር ምሕረቱን በሚፈሩት ላይ አጠነከረ።
ምሥራቅ ከምዕራብ እንደሚርቅ፥
እንዲሁ ኃጢአታችንን ከእኛ አራቀ።
አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል፤





እንደምን አደራችሁ አረፈዳችሁ ቤተሰብ💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

10 Nov, 13:31


ተመለሺ ሱላማጢስ ተመለሽ


ዘማሪት ቤተልሔም

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

10 Nov, 09:13


በአንዲት ቤተ ክርሲቲያን እናምናለን!!!




ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ



መልካም ዕለተ ሰንበት ይሁንላችሁ ቤተሰብ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Nov, 07:25


ይህች ጽዋ ከእኔ ትለፍ
ማቴ 26÷39
ጥቅምት 27/2013ዓ.ም የተሰጠ ትምህርት




በርእሰሊቃዉንት አባ ገብርኪዳን ግርማ💖




መልካም ቀን ቤተሰብ


እናዳምጥ👆

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Nov, 07:01


እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰራት ቅዱስ መላዕክ ማን ይባላል?

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Nov, 06:31


🤔 የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ⁉️

📌 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
📌 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
📌 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ
📌 ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
📌 ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
📌 ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
📌 ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ
📌 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
📌 ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
📌 ዘማሪ ዲ/ን ሮቤል ማቲያስ
📌 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ
📌 ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
📌 ዘማሪት አቦነሽ አድነው
📌 ዘማሪት ዶ/ር ሔለን ተስፋዬ

እና የሌሎችንም ...........

ዘማሪዎችን መዝሙሮች እና አዳዲስ
መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር OPEN
የሚለውን ይጫኑት። 👇

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Nov, 04:20


📚 ውዳሴ ማርያምን የደረሰው ሊቅ ስም ማን ይባላል



✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

06 Nov, 03:54


"ወዳጄ ሆይ  ሮማውያን ወታደሮች ጎንጉነው  በጌታችን እራስ ላይ  እሾህ እዳቀዳጁት  ባሰብህ ጊዜ  እጅግ ማዘንህ አይቀርም ። ሆኖም አንተም እሾህ የተባለውን አንድ ኃጢአት በሰራህ ቁጥር  በጌታችን ላይ  የተደፉትን እሾኾች ቁጥር እንደጨመርህ አስብ ።በፈጣሪ የማያምኑት ሮማውያን  ወታደሮች ከጎነጎኑት  እሾኽ በላይ  የጌታችንን እራስ የበለጠ ዘልቆ የሚወጋው  ደሙን አፍስሶ ያዳነን  እኛ ክርስቲያኖች በኃጢአታችን  የምንጎነጉነው  የእሾኽ አክሊል ነው ።{ስለመተላለፋችን የቆሰለው አምላክ በመተላለፋችንም ይቆስላል ።!}

{በእርሱ ቁስል እኛ ተፈወስን ከሚለው ርዕስ የተወሰደ )

[  ሕማማት]
{በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ}

መድኃኔዓለም  ሆይ አባት ሆይ ይቅር በላቸው በማለት በታላቅ ቃል በመስቀል ላይ ፥ ለተናገረ ቃልህ ሰላም እላለሁ በመስቀል ላይም በሰቀሉህ ጊዜና ጎንህን በጦር በወጉ ጊዜ አንዳችም የተቃውሞ ትንፋሽ ላልተነፈሰ እስትንፋስህም ሰላም እላለሁ ።
መድኃኔዓለም ሆይ ጻድቃንን ያይደለ ኃጥአንን ለማዳን በራሱ ደም ራሱ ለተጥለቀለቀ ስነ መልክህ ሰላም እላለሁ !

     ( መልክአ - መድኃኔአለም )27

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Nov, 20:34


#ጥቅምት_27

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥቅምት ሃያ ሰባት በዚህች ዕለት #የአምላካችን_የመድኃኔዓለም የስቅለቱ መታሰቢያ ነው፣ #የጻድቁ_አባ_መብዓ_ጽዮን የቃልኪዳን ቀን፣ የማህሌተ ጽጌ ደራሲው #አባ_ጽጌ_ድንግል_ዘወለቃ የእረፍታቸው መታሰቢያ ነው፣ ቅዱስ አባት የሀገረ ቃው #ኤጲስቆጶስ_አባ_መቃርስ አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#መድኃኔዓለም (በዓለ ስቅለት)

ጥቅምት ሃያ ሰባት በዚህች ዕለት የአምላካችን የመድኃኔዓለም የስቅለቱ መታሰቢያ ነው።

መድኃኒታችን ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና በቸርነቱ ስለኹላችን ድኅነት ሲል ራሱን ወድዶ ፈቅዶ ለሞት አሳልፎ በመስጠት ፍጹም ፍቅሩን አሳይቶናል። በቅዱስ ወንጌልም እርሱም መድኃኒታችን " ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር የለም" ብሎ ነግሮናል። እውነት ነው፣ ራስን ነፍስን ስለጠላት ነፍስ አሳልፎ ከመስጠት በላይ ምን ድንቅ ነገርና ምን ድንቅ ፍቅር አለ?

ቸሩ አምላካችንን የአስቆሮቱ ይሁዳ ሊያስይዘው የሊቃነ ካህናቱን አገልጋዮች እየመራ አመጣቸው። እነርሱንም ማንን ትፈልጋላችሁ ሲላቸው የናዝሬቱ ኢየሱስን አሉት፣ እኔ ነኝ ቢላቸው የቸሩን አምላክ ድምጽ ሰምቶ አይደለም መቆም በሕይወት መጽናት የሚቻለው የለምና ወደ ኋላቸው ተስፈንጥረው ወደቁ። ደጋግሞም እንዲህ ኾነ። በኋላ ግን እኔ ነኝ ብሎ በፈቃዱ ይሁዳ ስሞ አሳልፎ ሰጣቸው።

ከያዙት በኋላ እያዳፉና እየጎተቱ በሰንሰለት አስረው ወደ ቀያፋና ሐና ግቢ ወሰዱት፣ እስከ ሦስት ሰዓትም አላሳረፉትም ሲያሰቃዩት አድረዋል፣ በራሱም ላይ ሰባ ሦስት ስቊረት ያለው ወደ ሦስት መቶ እሾኾችን የያዘ የእሾህ አክሊል ጎንጉነው ቢያደርጉበት የራስ ቅሉን ቀዶ ገብቶ እስከ ልቡ ዘልቋል። እንደምን ጭንቅ ነው? እንዲህም አድርገው ደግሞ እያፌዙ ርኲስ ምራቃቸውን ይተፉበትና በዘንግም ደጋግመው ይመቱት ነበር። እየተፈራረቁ ያለ ምንም ርኅራኄ ቸሩን አምላክ ሥጋው እየተቆረጠ እስኪወድቅ ድረስ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት ጽኑዕ ግርፋትን ገርፈውታል። የገረፉበትም ጅራፍ በላዩ ላይ ሥጋን እየጎመደ የሚጥል፣ ሕመሙ አንጀት ሰርሥሮ የሚገባ በስለት የተያያዘበት ነበር።

በኋላም አላሳረፉትም እንዲህ አድርገውትም በሊቶስጥራ አደባባይ ያንን ዕርጥብ መስቀል አሸክመው ወደ ቀራንዮ ወሰዱት። እርሱ ግን ይህን ኹሉ ግፍ ሲያደርሱበት አንድም አልተናገረም ነበር። በቀራንዮም በአምስት ጽኑዕ ቅንዋት (ሳዶር፣ አላዶር፣ ዳናት፣ አዴራ እና ሮዳስ) ቸንክረው ዕርቃኑን ሰቀሉት።

በዚህች ቀን ድንግል ማርያም ልቧ በሐዘን ተሰበረ መጽናናትንም አልፈለገች ነበር፤ ወዳጁ ቅዱስ ዮሐንስም ፍፁም ለቅሶን አለቀሰ እናቱንም እናት ትሆነው ዘንድ በእግረ መስቀሉ አደራን ተቀበለ። ቅዱሳት አንስት በፍጹም ሀዘንና በዋይታ ዋሉ። በስልጣኑም ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋው ለየ። ሰባት ድንቅ የኾኑ ተአምራትንም አድርጎ አምላክ መኾኑን ገለጠ። ይህም ጽኑዕ የኾነ ለሰማይ ለምድር የከበደ ነገር ሲከሰት ፀሐይ አምላኬን ዕርቃኑ እንዴት አያለሁ ብላ ጨለመች። ጨረቃ ደም ኾነች፣ ከዋክብቱም ረገፉ፣ ንዑዳን ክቡራን ንጹሐን መላእክትም ትዕግስቱን እያደነቁ በጽኑዕ ሐዘንና መደነቅ ከቅዱስ ዕፀ መስቀሉ ፊት እንደሻሽ ተነጠፉ።

አስራ አንድ ሰዓት በሆነም ጊዜ ዮሴፍና ኒቆዲሞስ ከታላቅ ክብርና ሐዘን ጋር ቅድስት ሥጋውን ከመስቀሉ አውርደው በክብር ገንዘው በአዲስ መቃብር ቀበሩት። በሦስተኛውም ቀን እንደተናገረ ተነሳ።

በዛሬዋ ቀን ቤተ ክርስቲያን የመድኃኔለምን የስቅለት በዓል በደማቁ ታከብራለች፤ ይህም የለውጥ በዓል ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ደሙን ያፈሰሰው ስጋውን የቆረሰው መጋቢት 27 ቀን ነው፤ ይህ በዓል ግን በዐቢይ ጾም ስለሚውል በዐቢይ ጾም ሀዘን እንጂ ደስታ ስለሌለና በዓል ማክበር ስለማይፈቀድ፤ ወደ ጥቅምት 27 ተዛውሮ ደስ ብሎን እንድናከብረው ቤተ ክርስቲያን ስርዓት ሰርታልናለች፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_መብዓ_ጽዮን

አባ መብዓ ጽዮን በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ልጅ በማጣታቸው በጾምና በጸሎት ፈጣሪያቸውን ከሚለምኑ ባልና ሚስት ተወለዱ። የንቡረ እድ ሳሙኤል ረባን የሆነው መብዓ ጽዮን አባቱ እስከ ዳዊት ያለውን ትምህርት አስተማረውና ዲቁናን ተቀበለ። ልጁ የትምህርት ዝንባሌ እንዳለው አባቱ ተረድቶ ቤተ ማርያም ከሚባለው ደብር ወስዶ ተክለ አማኅጸኖ ከሚባል የቅኔ መምህር ዘንድ አስገባው። በዚያም ቅኔና እና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን እውቀቶችን ገበየ። ከዚህም በተጨማሪ ሥዕል መሳልና ጽሕፈት መጻፍ ተማረ።

መብዓ ጽዮን የልጅነቱን ዘመን ሲፈጽም ‹‹ለነፍሳቸው ድኅነት ዋጋ ያገኙ ቅዱሳን ብዙ ናቸው።በመጾም ያገኙ አሉ፤ በትምህርት ያገኙ አሉ፤ በድካም ያገኙ አሉ፤ በጸሎት በትጋት ያገኙ አሉ፤ እኔ ግን የጌታዬን የኢየሱስ ክርስቶስን የሞቱን መታሰቢያ ማድረግ ይገባኛል። በዚህም ፊቱን አያለሁ፤ እርሱ ጌታ ለደቀመዛሙርቱ "የትንሣኤዬን መታሰቢያ ብታደርጉ የሞቴን መታሰቢያ አድርጉ ብሏልና" በማለት ፍላጎቱ በምንኩስና በመኖር ፈጣሪን ማገልገል መሆኑን ለወላጆቹ ገለጸላቸው።

አባትና እናቱም "ፈጣሪህን ለማገልገል ኅሊናህ ከአሰበ እሺ፤ በጀ ደስተኛ ነን" ብለው ፈቀዱለት። ከዚያም መብዓ ጽዮን ዳሞት አባ ገብረክርስቶስ ወደሚባል መነኩሴ በመሄድ መነኮሰ። አባ መብዓ ጽዮን አባ ገብረክርስቶስ ጋር በመቀመጥ ሥርዓተ ምንኩስናን ካጠኑ በኋላ ከአባ ገብርኤል ዘንድ ሄደው የቅስናን ማእረግ ተቀበሉ። ከዚያም በኋላ በአበው ሕግ በምንኩስና ተወስነው፤ በበአታቸው ሆነው ‹‹ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የዕለተ ዓርቡን መከራህን አሳየኝ፤ ስለራሴ ፈጽሞ አለቅስ ዘንድ›› ብለው በጸልዩ ጊዜ ‹‹መከራ መስቀሉን ለማየት ትፈቅዳለህን?›› ብሎ ጠየቃቸው። ጻድቁ አባ መብዓ ጽዮንም ‹‹አዎ አይ ዘንድ እወዳለሁ›› ሲሉ ለጌታቸው መለሱለት። ያን ጊዜም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዕፀ መስቀል ተተከለ። በመስቀሉ ላይም እጆቹና እግሮቹ ተቸንክረውና ተዘርግተው ታዩ ፤በራሱ ላይም የእሾህ አክሊል ደፍቶ ነበር።

እንዲህ ሆኖ በሮም አደባባይ ለቅዱስ ጴጥሮስ እንደታየው ጌታችን ለአባ መብዓ ጽዮንም ታያቸው። ከዚህም በኋላ አባ መብዓ ጽዮን የጌታችን የመድኃኔዓለምን ሕማሙን፣ መከራውን፣ ግርፋቱን፣ እስራቱን በጠቅላላ ፲፫ቱን ሕማማተ መስቀል በማሰብ ጀርባቸውን በአለንጋ ይገርፉ ፤ራሳቸውንም በዘንግ ይመቱ ነበር። የጌታን መከራ መስቀል እያሰቡ ዐይኖቻቸው አስከሚጠፉ ድረስ ያለቅሱ ነበር ። ጌታችን ግንደ መስቀሉን (የመስቀሉን ግንድ) አንደተሸከመ በማሰብ ትልቅ ድንግያ ተሸክመው ይሰግዱ ነበር። መራራ ሐሞት መጠጣቱን በማሰብ ዓርብ ዓርብ ኮሶ ይጠጡ ነበር። የጌታ ደቀመዝሙር ዮሐንስ ወንጌላዊ ጌታ በተሰቀለ ጊዜ አብሮ ስለነበርና ዐይን በዐይን ስለተመለከተ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ መስቀል እያሰበ ፸ ዘመን ፊቱን በሐዘን ቋጥሮ እንደኖረ ሁሉ ጻድቁ አባ መብዓ ጽዮንም እንደ ዮሐንስ ወንጌላዊ የጌታችንን መከራ መስቀል እያሰቡ ከዓለም ተድላና ደስታ ተለይተው በትምህርት ፣ በትሩፋት ፣ በገድል ጸንተው ኖረዋል። ጻድቁ መብዓ ጽዮን በሕይወተ ሥጋ ዘመናቸው የላመ የጣመ እንዳልተመገቡ፤በፈረስ በበቅሎ እንዳልሄዱ፤አልጋ ላይ እንዳልተኙ፤ገድላቸው ያስረዳል። የክርስትናን ትምህርት ለጋፋት ሰዎች እንዲስፋፋ ያደረጉት አባ መብዓ ጽዮን የጌታን ሕማማተ መስቀል እያሰቡ ዘወትር ስለሚያነቡ ዐይኖቻችው ጠፍተው ነበር። ነገር ግን እመ ብዙኃን የሆነችው ቅድስት ድንግል ማርያም ወደኚህ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Nov, 20:34


ጻድቅ አባት በአት የብርሃን ጽዋ ይዛ መጥታ ዐይኖቻቸውን ቀብታ አድናቸዋለች። ከዚህ የተነሳ በትረ ማርያም እየተባሉ ይጠሩ አንደነበር ገድላቸው ያስረዳል።

የጻድቁ መታሰቢያ በዓል በየዓመቱ ጥቅምት ፳፯ ቀን ከመድኃኔዓለም የስቅለት በዓል ጋር ይከበራል። ጥቅምት ፳፯ ቀን ለወዳጆቹ እውነተኛውን ዋጋ የሚከፍል መድኃኔዓለም ክርስቶስ ለጻድቁ አባ መብዓ ጽዮን ብዙ ቃል ኪዳን የገባበት ቀን ነው።

የአቡነ መብዓ ጽዮን ረድኤታቸው፣ በረከታቸውና አማላጅነታቸው አይለየን፤አሜን!!!

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ጽጌ_ድንግል_ዘወለቃ

በ14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረ ሊቅ ሲኾን፤ አባ ጽጌ ድንግል (ጽጌ ብርሃን) ሀገሩ ይፋት ሃይማኖቱ ኦሪት ነበረ፡፡ በንጉሥ ሰሎሞን ፈቃድና በካህኑ አዛርያስ መሪነት የብሉያት መጻሕፍትን ከዕብራይስጥ ወደ ግእዝ ተርጕመው ሊያስተምሩ፣ ታቦተ ጽዮንን ከኢየሩሳሌም ይዘው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡትና የብሉያት መጻሕፍት ሊቃውንት ከነበሩት ከ318 ሌዋውያን (ከቤተ እስራኤላውያን) ነገድ ነው፡፡ የተወለደውም በሰሜን ሸዋ በይፋት አውራጃ ውስጥ ሲሆን፤ መጀመርያ ኢእማኒ (ያላመነና ያልተጠመቀ) ነበር።

ከዕለታት አንድ ቀን ይህ ሰው፤ በወጣትነት ዕድሜው አውሬ ለማድን ወደ ጫካ ሄደ፣ ጫካዋም በዚያው በይፋት አውራጃ የምትገኝና ልዩ ስሟ ደንስ (ገዳመ ደንስ) ትባላለች፣ በጫካዋ ውስጥም ፊቷ በጽጌረዳ አበባ የተከበበና ያጌጠ፣ እጅግም ደስ የምታሰኝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን ሥዕል አይቶ በሥዕሏ ውበት እየተደነቀ ሥዕሏን ሲመለከት እንደ እርሱ ያልተጠመቀ ጓደኛው መጥቶ፣ "ምን እየፈለግህ ነው? የክርስቲኖችን ሥዕል ነውን?" ብሎ ለድንግል ማርያም ምስጋና ይግባትና በያዘው በትር ሥዕሏን ሲመታት ወዲያው ተቀሥፎ ሞተ። ከዚህ በኋላ ክንፎቹ በጽጌረዳ አበባ ያጌጡ የመሰለ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል በነጭ ወፍ ተመስሎ ወደ እርሱ መጥቶ አንድ ቀይ መነኩሴ እሰኪመጣ ድረስ፣ ይህችን ሥዕል ጠብቃት ብሎ በሰው አነጋገር ነግሮት ተሠወረ።

የአቡነ ዜና ማርቆስ የገድል መጽሐፍ፣ እንደሚናገረው ካህን ከነበረው ከአባቱ ከዘርዐ ዮሐንስ አና ከእናቱ ማርያም ዘመዳ በ1262 ዓ.ም. ኅዳር 24 ቀን በሰሜን ሸዋ ግዛት በሚገኘውና ልዩ ስሙ እቲሳ ቅዱስ ሚካኤል በሚባለው አጥቢያ የተወለደው አቡነ ዜና ማርቆስ ደብረ ብስራት ከሚባለው ገዳሙ ወደ ይፋት መጥቶ ከነብዩ ኢሳይያስ ትንቢት ከምዕ. 11፥1 ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ እያለ በግእዝ ቋንቋ ሲያነብ አባ ጽጌ ድንግል በሰማ ጊዜ አባቶቼ አይሁድ የነቢያትን ትንቢት ንባቡን አስተምረውኛል አውቀዋለሁ፤ ትርጕሙን ግን አላውቀውምና ተርጕምልኝ አለው፡፡

አቡነ ዜና ማርቆስም ሲተረጕምለት እንዲህ አለ፤ ትወጽእ በትር እምሥርወ እሴይ፣ የሚለው ንባብ ከእሴይ ነገድ የሕይወት በትር የኾነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ትወለዳለች ማለት ነው፡፡ ወየዐርግ ጽጌ እምኔሃ የሚለው ንባብ ደግሞ፤ እመቤታችን ተወልዳ፣ ከእርሷም ጌታ በድንግልና ይወለዳል፣ ከጌታም ክብር ይገኛል ማለት ነው፣ ይህም ጌታ ተወልዶ ትንቢቱ በእውነት ተፈጽሟል ብሎ ተረጐመለት፡፡ ኢሳ 7፥14፣ ማቴ18፥24፡፡

ይህ ሰውም (አባ ጽጌ ድንግልም) በዚህ ትርጕም ደስ ተሰኝቶ አባት ሆይ የኢሳይያስን ትንቢት በመልካም ሁኔታ ተረጐምከው፣ መልካም ነገርንም ተናገርክ አለውና፣ ሥዕሏ ወዳለችበት ቦታ ወስዶ ታሪኩ ከላይ እንደተገለጸው፣ በጫካ ውስጥ ያያትን ሥዕል ጓደኛው በያዘው ብትር ሲመታት ወዲያውኑ እንደተቀሠፈና ክንፎቹ በጽጌረዳ አበባ ያጌጡ፣ "አንድ ነጭ ወፍ /ቅዱስ ሩፋኤል/" ወደ እርሱ መጥቶ ቀይ መነኵሴ እስኪመጣ ድረስ ይህችን ሥዕል ጠብቃት ብሎ በሰው አነጋገር ያነጋገረውን ሁሉ ነገረው፣ አቡነ ዜና ማርቆስም ከሥዕሏ የተደረገውን ተአምር ሰምቶ፣ እጅግ ደስ አለውና በል መጀመሪያ እመቤታችን በድንግልና በወለደችው በፈጣሪ ልጇ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን ይህችን ሥዕል ያስገኘ፣ ሰማይና ምድርን፣ በውስጣቸው ያለውንም ሁሉ የፈጠረ፣ እርሱ እንደኾነ እውቅ አለውና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቆ ጽጌ ብርሃን ብሎ ሰየመው፡፡

ከዚህ በኋላ ሥዕሏን በገዳመ ደንስ ደብረ ብሥራት ወደሚባለው ገዳም ወስዶ በዘመነ ጽጌ ጥቅምት አንድ ቀን በክብር አስቀመጣት የምትከብርትንም ቀን ጥቅምት 3 እና ሰኔ 8 ቀን አደረገ፡፡

አቡነ ዜና ማርቆስም ጽጌ ብርሃንን ለመዓርገ ምንኵስና አበቃው፤ የአባ ጽጌ ብርሃንም ጽጌ ድንግል የሚል ቅጽል ስም አለው፣ በማኅሌት አገልግሎት ጊዜም ታላቁ ጻድቅ አቡነ ዜና ማርቆስ ቤተ ክርስቲያኒቱንና ሥዕሏን እየዞረ ሲያጥን፣ እመቤታችን የካህናቱን አገልግሎት እንደምትባርክ፣ ካህናቱ በግልጽ ይረዱ ነበር፣ አባ ጽጌ ብርሃንም ከመጠመቁ በፊት በአባቶቹ በአይሁድ ሥርዓት እያለ የብሉያት መጻሕፍትን የተማረ ነበር፣ የሐዲሳት መጻሕፍት ትርጓሜን ግን ከአቡነ ዜና ማርቆስ ተማረ እስከ ምድር ዳርቻ ድረስ ላሉ አሕዛብ ሁሉ የድኅነት ምክንያት ትሆኑ ዘንድ ብርሃናቸው፣ መምህራቸው አደረግኋችሁ ብሉ ጌታ ነቢዩ ኢሳይያስንና ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስን እንደመረጣቸው፣ ኢሳ 49፥6.፣ የሐ.ሥራ13፥47 ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ዜና ማርቆስ ስብከተ ወንጌልን እንደ ዕለት ጉርስና እንደ ዓመት ልብስ አድርጎ፣ መላ ኢትዮጵያን ዞሮ፣ አስተምሮና ባርኮ የዕድሜ ባለጸጋም ሆኖ በተወለደ በ140 ዓመት በ1402 ዓ.ም ታኅሣሥ 3 ቀን ፣ ዐርብ ጠዋት ዐረፈ፡፡

አባ ጽጌ ብርሃንም በወሎ ክፍለ ሀገር በወራይሉ አውራጃ፣ ልዩ ስሙ ደብረ ሐንታ ለሚባለው ገዳም የሕግ መምህር ሆኖ ከተሸመውና ከጓደኛው ከአባ ገብረ ማርያም ጋር እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ በመሆን፣ እመቤታችንንና ፈጣሪ ልጇን በጎ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየመሰለ የሚያመሰግነውን ማኅሌተ ጽጌ የተባለውን ድርሰት፣ በአባቷ በዳዊት መዝሙር መጠን 150 አድርጎ ደረሰ፡፡ ፍሬ ከአበባ አበባም ከፍሬ እንደሚገኝ ኹሉ በማኅሌተ ጽጌ እመቤታችንን በአበባ፥ ጌታችን በፍሬ፤ ወይም እመቤታችንን በፍሬ፥ ጌታችን በአበባ እየተመሰሉ የሚመሰገኑበት ምስጋና ነው። ሰቈቃወ ድንግል ማለት እመቤታችን ከልጇ ከመድኀኔዓለም፣ ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር በስደቷ ወቅት ያየችውን መከራ፥ ልቅሶ ዋይታ የሚዘከርበት የማኅሌተ ጽጌ አርኬ ነው፡፡

(የሰቈቃወ ድንግልን ደራሲ በተመለከተ አባ ጽጌ ድንግል ደረሱት የሚሉ አሉ፤ በሌላ በኩል ደግሞ አባ ገብረ ኢየሱስ ዘገዳመ መጕና /አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ/ ወይም /አባ አርኬላዎስ/ ነው የደረሱት የሚሉም አሉ፡፡)

ፍቅር ለባልንጀራው ክፉ የማያደርግ የሕግ ፍጻሜ ነውና፤ ሮሜ 13፥10-11፣ አባ ጽጌ ብርሃንና አባ ገብረ ማርያምም የዘመነ ጽጌ የማኅሌት አገልግሎትን ሳይለያዩ በሰላምና በፍቅር (በአንድነት) አገልግለዋል፣ ማለትም አንድ ዓመት አባ ገብረ ማርያም የክረምት መውጫና የዘመነ ጽጌ ዋዜማ በሆነው መስከረም 25፣ ቀን ከደብረ ሐንታ መጥቶ ገዳመ ጽጌ (ደብረ ብሥራት) ገብቶ ከመስከረም 26 ቀን እስከ ኅዳር 5 ቀን ያለውን የዘመነ ጽጌ የ40 ቀን አገልግሎትን ከአባ ጽጌ ብርሃን ጋር ፈጽሞ ኅዳር 8 ቀን ወደ ደብረ ሐንታ ይመለሳል፤ በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ አባ ጽጌ ብርሃን ከገዳመ ጽጌ (ከደብረ ብሥራት) ወደ ደብረ ሐንታ ሄዶ እንደዚሁ እንደ አባ ገብረ ማርያም 40ውን ቀን አገልግሎ ይመለሳል፣ እኒህ ሁለቱ ቅዱሳን ሊቃውንትም ታሪኩ ከላይ እንደተገለጸው እንዲህ እያደረጉ እስከ ዕለተ ዕረፍታቸው ድረስ በፍቅርና በትሕትና

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Nov, 09:30


ሰላምን የሚያደርጉ ብጹዓን ናቸው
ክፍል 1






በእርሰ ሊቃዉንት አባ ገብረኪዳን ግርማ💖


በቸር ዋሉ ቤተሰብ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

05 Nov, 06:33


"ብዙ ጊዜ ሰዎች ብልህ ነን እያሉ ይሳሳታሉ። ነገር ግን ብልህ የሚባሉት ብዙ የተማሩና ብዙ ያነበቡ ብዙ የሚናገሩ ብቻ አይደሉም። ይልቁንም ጠቢባን የሚባሉት ጥብብት መጥበቢት ብልህ ነፍስ ያላቸው፤ የእግዚአብሔርንና የሰይጣንን ለይተው ለእግዚአብሔር ሆነው የሚኖሩ ናቸው። ፍጹም ምልዓተ ኃጢአትንና ከጦር ይልቅ የሚወጉ የኃጢአት እሾሀቸውን የነቀሉ ናቸው ጠቢባን።

ጠቢባንስ እግዚአብሔርን ያለጥርጥር በሙሉ ልብ የሚያምኑት፤ አምነውም እንደ ፈቃዱ የተከተሉት፤ በክንፈ ጸጋ ተመስጠው ከልብ በሚወጣ ውዳሴ ከእርሱ ጋር ተዋሕደው የሚኖሩ ናቸው። የነፍሳቸውን ረብሕ ጥቅም አውቀው ዕለት ዕለት ያንን የሚለማመዱ በእውነት ጠቢባን እነዚህ ናቸው።"

#ቅዱስ አባ እንጦንስ

💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

31 Oct, 08:03


ሰዎች ላይ እንዳልፈርድ ምን ላድርግ?




በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ

💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

31 Oct, 03:47


ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እናቶች አባቶች እህት ወንድሞች እንደምን አደራችሁ አረፈዳችሁ ይቺን ማለዳ እንድናይ የፈቀደዉ አምላካችን ስለ ማይነገር ስጦታዉ እግዚአብሔር ይመስገን❤️


እንኳን ለእመቤታችን ወርኃዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን የእመቤታችን ጣዕም ፍቅሯ በረከቷ ረድኤቷ አይለየን

አሜን


💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

30 Oct, 20:09


#ጥቅምት_21

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥቅምት ሃያ አንድ በዚህችም ቀን #እመቤታችን_ተአምራትን_አድርጋ_ሐዋርያው_ማትያስን ከእሥራት ቤት ያወጣችበት፣ #የነቢይ_ኢዩኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ፣ የማርታና የማርያም ወንድም #የቅዱስ_አልዓዛር ሥጋው ከቆጵሮስ አገር የፈለሰበት፣ የቅዱስ አባት #አባ_ዮሐንስ ዘኢየሩሳሌም እረፍት ነው፣ ታላቁ ጻድቅ #አቡነ_አላኒቆስ ዕረፍታቸው ነው፡፡

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#እመቤታችን_ለሐዋርያው_ማትያስ_ያደረገችለት_ተአምር

በዚህችም ቀን እመቤታችን ማርያም ተአምራትን አድርጋ ደቀ መዝሙር ማትያስን ከእሥራት ቤት አዳነችው።

የከበሩ ቅዱሳን ወንጌልን በዓለም ዞረው ይሰብኩ ዘንድ ዕጣ ሲጣጣሉ ለቅዱስ ማትያስ ዕጣ የደረሰው ሰውን ወደሚበሉ ሰዎች አገር ነበር፡፡ ይህችም ሀገር እስኩቴስ የተባለች ሩሲያ እንደሆነች የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች ፍንጭ ሰጥተዋል፡፡

ማትያስም እነዚህ ሰውን የሚበሉ ሰዎች አገራቸው እንደደረሰ ዐይኑን አውልቀው አሠሩት፡፡ ምግባቸውም የመጻተኛ ሰው ሥጋ ነው፡፡ በልማዳቸው መሠረት መጻተኛን ሰው ገና እንደያዙት ዐይኖቹን ዐውልቀው በእሥር ቤት ያኖሩታል፡፡ እስከ 30 ቀንም ድረስ ሳር እያበሉ ያስቀምጡትና በ30ኛው ቀን አውጥተው አርደው ይበሉታል፡፡

ሐዋርያው ማትያስንም በልማዳቸው መሠረት ዐይኖቹን አውልቀው አሠሩት፡፡ ሐዋርያውም በእሥር ቤት ሆኖ በዚያ ላይ ዐይኖቹን ታውሮ ሳለ በጭንቅ ወደ ጌታችንና ወደ እመቤታችን ይለምን ነበር፡፡ ነገር ግን እመብርሃንና ልጇ መድኃኔዓለም 30ኛው ቀን ሳይፈጸም ሐዋርያው እንድርያስን ወደ እርሱ ላኩለት፡፡ ማትያስም ዐይኑን ፈወሱለትና ማየት ቻለ፡፡

እንድርያስም በተዘጋው በር በተአምራት ገብቶ አሥርቤቱ ውስጥ ያሉ እሥረኞችን በስውር አውጥቶ ከከተማው ውጭ ካስቀመጣቸው በኋላ ሁለቱ ሐዋርያት ተመልሰው ሰውን ለሚበሉት ሰዎች ተገለጡላቸው፡፡ እነርሱም ይዘው በአንገታቸው ገመድ አግብተው ለ3 ቀን በሀገራቸው ጎዳናዎች ላይ ሁሉ ጎተቱዋቸው፡፡ ሁለቱም ሐዋርያት በጸሎታቸው ከእሥር ቤቱ ምሰሶ ሥር ውኃ አፈለቁና ውኃው ሀገራቸውን ሁሉ እስኪያጥለቀልቅና ሰዎቹንም እስከ አንገታቸው ድረስ እስከሚደርስ ሞላ፡፡ ሁሉም በተጨነቁ ጊዜ ሁለቱ ሐዋርያት በፊታቸው ተገለጡና ‹‹በጌታችን እመኑ ትድናላችሁ›› በማለት ወንጌልን ሰብከውላቸው አሳመኗቸው፡፡ ምሥጢራትንም ሁሉ ገለጡላቸው፡፡ ደግሞም የአራዊት ጠባይን ከሰዎቹ ያርቅላቸው ዘንድ ወደ ጌታችንና ወደ ተወደደች እናቱ ከጸለዩ በኋላ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቋቸው፡፡ ያ የአውሬነት ጠባያቸውም ጠፍቶላቸው የዋህ፣ ቅንና ሩኅሩኆቸ ሆኑ፡፡ ሐዋርያትም ሃይማኖትን እያስተማሯቸው 30 ቀን አብረዋቸው ከተቀመጡ በኋላ አገልጋይ ኤጲስ ቆጶሳትን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን ሾመውላቸው ወደ ሌላ ሀገር ሄዱ፡፡

ለሐዋርያት ሞገሳቸው ጣዕመ ስብከታቸው የኾነች ክብርት እመቤታችን ለእኛም ትለመነን!

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ኢዩኤል_ነቢይ

ዳግመኛም በዚህችም ቀን የነቢይ ኢዩኤል የዕረፍቱ መታሰቢያ ሆነ። ይህም የእስራኤልን ልጆች የሚያስተምርና የሚገሥጻቸው ነበር ስለ ክርስቶስም በኢየሩሳሌም መኖርና ማስተማር ትንቢት ተናገረ። ደግሞም ስለ መከራው በሐዋርያትና በሰባ ሁለቱ አርድእት በሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስት ላይ የመንፈስ ቅዱስን መውረድ እንዲህ ሲል ተናገረ።

ከዚህ በኋላ በሥጋዊ በደማዊ ሰው ሁሉ ከመንፈሴ አሳድርበታለሁ ሴቶች ልጆቻችሁና ወንዶች ልጆቻችሁ ትንቢትን ይናገራሉ አለቆቻችሁ ሕልምን ያልማሉ ጎልማሶቻችሁም ራእይን ያያሉ። ሁለተኛም እንዲህ አለ ያን ጊዜ ከተራራው ማር ከኮረብታውም ወተት ይፈሳል በቤተ እግዚአብሔር አጠገብ ካሉ ከይሁዳ አገሮች ሁሉ ምንጩ ከላይ ወደታች ይፈሳል።

ሙታን በሚነሡ ጊዜ ስለሚሆነው የፍርድ ሰዓት እንዲህ አለ ፀሐይና ጨረቃ ይጨልማሉ የከዋክብትም ብርሃናቸው ይጠፋል። የትንቢቱንም ወራት አድርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አልዓዛር የማርታና የማርያም ወንድም

በዚችም ቀን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ከሙታን ያስነሣው የቅዱስ አልዓዛር ሥጋው ከቆጵሮስ አገር የፈለሰበት ሆነ።

ከክርስቲያን ነገሥታትም አንዱ ሥጋው በቆጵሮስ እንዳለ በሰማ ጊዜ ከቆጵሮስ ደሴት ወደ ቊስጥንጥንያ አፈለሰው። ሊአፈልሱትም በወደዱ ጊዜ በከበረ የደንጊያ ሣጥን ውስጥ ሁኖ በምድር ውስጥ ተቀብሮ አገኙት በላዩም እንዲህ የሚል ጽሑፍ ነበረ ይህ በመቃብር ውስጥ አራት ቀን ከኖረ በኋላ ከሙታን ለይቶ ላስነሣው ክብር ይግባውና የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወዳጁ የሆነ የቅዱስ አልዓዛር ሥጋ ነው።

ይህንንም በአዩ ጊዜ ደስ ተሰኙበት ተሸክመውም ወደ ቊስጥንጥንያ አገር ወሰዱት ካህናቱም ሁሉ ወጥተው በታላቅ ክብር በመዘመርና በማመስገን ተቀበሉት በአማረ ቦታም አኖሩት በዚችም ቀን በዓልን አደረጉለት።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘኢየሩሳሌም

በዚህችም ቀን ለከበረች አገር ኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት የሆነ ቅዱስ አባት አባ ዮሐንስ እግዚአብሔርን በሚወድ የንጉሥ ሰይፈ አርዕድ ደግሞ ቈስጠንጢኖስ ለሚባል ልጁ በሆነ በንጉሣችን በዳዊት ዘመን አረፈ።

ይህም ቅዱስ ከምስር አገር ታላላቆች እግዚአብሔርን የሚፈሩ የክርስቲያኖች አባቶች ልጅ ነው። የዲቁና መዓረግንም ለመሾም እስከ ተገባው ድረስ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት እያስተማሩ በበጎ አስተዳደግ አሳደጉት። ከዚህም በኋላ በዲቁናው ሹመት አገልግሎቱን በአሳመረ ጊዜ የቅስና መዓረግ የሚገባው ሁኖ ቅስና ተሾመ።

በጾም በጸሎት እግዚአብሔርንም በመፍራት የተጠመደ ሁኖ ድኆችንና ችግረኞችን የሚወዳቸው የሚረዳቸው ሆነ ያን ጊዜ የሐዋርያት የሆነች የጵጵስና ሹመት የምትገባው ሁና በከበረች አገር በኢየሩሳሌም በእግዚአብሔር ፈቃድ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ ሕዝቡንም በፈሪሀ እግዚአብሔርና በትሕትና የሚያስተምራቸው ሆነ።

እነርሱም ስለ ቅድስናው እጅግ የሚወዱት ሆኑ መልኩና የአንደበቱ አገላለጥ እንደ እግዚአብሔር መልአክ ያማረ ነበር። በሹመቱም ጥቂት ዘመናት ከኖረ በኋላ ከመንበረ ሢመቱ እስከ አራቀው ድረስ በላዩ ሰይጣን ምክንያትን አመጣ።

ይህም እንዲህ ነው በእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት በአባ ማርቆስ ዘመን በግዛቱ ውስጥ ያሉ እስላሞች ስለ ዐመፁበት የኢትዮጵያ ንጉሥ ፈጅቷቸው ነበርና ስለዚህ በግዛቱ ውስጥ በሚኖሩ እስላሞች ላይ ክፉ እንዳያደርግ ለኢትዮጵያ ንጉሥ መልእክት እንዲልክ ሊቀ ጳጳሳት አባ ማርቆስን የምስር ንጉሥ አዘዘው።

አባ ማርቆስም ወደ ኢትዮጵያ ንጉሥ ስለሚላኩ ሰዎች ከመኳንንቱ ከኤጲስ ቆጶሳቱና ከሀገር ታላላቆች ሽማግሌዎች ጋር ተማክሮ እሊህን ብሩሀን ከዋክብት የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳሳት አባ ዮሐንስን የምስር ኤጲስቆጶስ አባ ሳዊሮስን በእውቀታቸው በአስተዋይነታቸውና በቅድስናቸው መረጡአቸው ወደ ኢትዮጵያ ንጉሥም ይሔዱ ዘንድ ግድ አሏቸው።

እነርሱም ታዛዦች ሁነው ወደ ኢትዮጵያ መጡ የኢትዮጵያ ንጉሥም መምጣታቸውን በሰማ ጊዜ እጅግ ደስ አለው እሊህንም ቅዱሳን አባቶች ይቀበሏቸው ዘንድ አሽከሮቹን በቅሎዎችን አስይዞ ላከ በመጡም ጊዜ በታላቅ ደስታ ሰላምታ አቀረበላቸው ከእርሳቸውም ቡራኬን ተቀበለ ታላቅ ክብርንም አከበራቸው ። እነርሱም የሊቀ ጳጳሳት አባ ማርቆስን ደብዳቤ ሰጡት እርሱም ተቀብሎ አንብቦ ለሊቀ ጳጳሳቱ ቃል ታዛዥ መሆኑን ገለጠላቸው።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

30 Oct, 11:22


በዐመጸኛው ገንዘብ ወዳጅ አብጁ
ክፍል 2




በርእሰሊቃዉንት አባ ገብረኪዳን ግርማ


መልካም ቀን

💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

29 Oct, 22:01


#ጥቅምት_20

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥቅምት ሃያ በዚህች ቀን ክቡርና ገናና የሆነ #የአባ_ዮሐንስ_ሐፂር እና የስሙ ትርጓሜ ጠባቂና አዳኝ የሆነ #የታላቁ_ነቢይ_ኤልሳዕ የዕረፍታቸው መታሰቢያ ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አባ_ዮሐንስ_ሐፂር

ጥቅምት ሃያ በዚህች ቀን ክቡርና ገናና የሆነ አባ ዮሐንስ ሐፂር አረፈ። የዚህ ቅዱስ ወላጆቹ ከላይኛው ግብጽ ናቸው እነርሱም እግዚአብሔርን የሚፈሩ ናቸው ግን ከእርሱ በቀር ልጅ የላቸውም የዚህ ዓለምም ብልጽግና ቢሆን የላቸውም ነገር ግን በበጎ ሥራ ባለጸጎች ናቸው ይህንንም ቅዱስ እያስተማሩ በበጎ አስተዳደግ አሳደጉት ።

የዚህም ቅዱስ ዕድሜው ዐሥራ ስምንት ዓመት ሲሆነው የእግዚአብሔር ቸርነት አነሣሥታው የመላእክት የሆነ አስኬማን ይለብስ ዘንድ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ ይኸውም የምንኵስና ልብስ ነው።

ከዚያም በደረሰ ጊዜ አባ ባይሞይ የሚባለውን አንዱን አረጋዊ አባት ተገናኘው ዮሐንስም ሰገደለትና ወደ እርስ እንዲቀበለው ለመነው ሽማግሌውም አባት ልጄ ሆይ ያንተ በዚህ መኖር ልክ አይደለም በዚች ገዳም የሚኖሩ በእጆቻቸው ይሠራሉ በቀንና በሌሊት ይጾማሉ ይጸልያሉ በሚተኙም ጊዜ ያለ ምንጣፍ በምድር ላይ ይተኛሉ አንተ ወጣት ጎልማሳ ስለሆንክ ይህን ሁሉ ችግር አትችልም። ነገር ግን ወደ ዓለም ተመልሰህ እንደ ሰው ሁሉ በጎ አኗኗርን ትኖር ዘንድ ይሻልሃል የዚች ገዳም ኑሮ ጭንቅ ነውና አለው።

አባ ዮሐንስም እንዲህ አለው እኔ በጥላህ ሥር ልኖር መጥቼአለሁና ስለ እግዚአብሔር ብለህ ተቀበለኝ እንጂ አትመልሰኝ ይህም አባ ባይሞይ እግዚአብሔርን ሳይጠይቅ ምንም ሥራ አይሠራምና በዚያን ጊዜ ሥራውን ይገልጥለት ዘንድ ስለ ዮሐንስ ሐፂር እግዚአብሔርን ለመነው የእግዚአብሔርም መልአክ ተገልጦለት እርሱ የተመረጠ መሳሪያ ይሆናልና ተቀበለው ብሎሃል አለው።

ከዚህም በኋላ ዮሐንስ ሐፂርን ወስዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን አስገባው የምንኵስና ልብሶችንም አምጥቶ በላያቸው ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ጸለየ ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጾ በመስቀል ምልክት በልብሶቹ ላይ አማተበ ሽማግሌውም እነዚያን ልብሶች ለአባ ዮሐንስ አለበሰው ።

ከዚያቺም ቀን ጀምሮ አባ ዮሐንስ ተጋድሎንና አገልግሎትን ጀመረ አባ ባይሞይም ሊፈትነው ወደደ በአንዲትም ቀን ደብድቦ ከአንተ ጋር መኖር አልሻም ብሎ ከበዓቱ አስወጥቶ አባረረው የከበረ አባ ዮሐንስም ከሜዳ መካከል በውጭ ቆመ በየቀኑም በጥዋት እየወጣ ከእዚህ ላይህ አልሻም እያለ ይመታዋል እርሱ ግን አባቴ ሆይ ይቅር በለኝ ብሎ ከእግሩ በታች ይሰግዳል ።

በሰባተኛዪቱም ቀን ወደ ቤተ ክርስቲያን ሊሔድ ሽማግሌው አባ ባይሞይ ወጣ አባ ዮሐንስንም ሰባት መላእክት ከበው አክሊላትን ሲያቀዳጁት አያቸው ከዚያንም ጊዜ ወዲህ መፈተኑን ተወው ወደ መኖሪያውም አስገባው።

ከዚህም በኋላ በአንዲት ቀን አባ ባይሞይ የደረቀ ዕንጨት አግኝቶ ወስዶ ለአባ ዮሐንስ ሰጠውና ይህን ዕንጨት ትከለው እስከሚበቅልና እስከሚአፈራ ድረስ ውኃን አጠጣው አለው ። አባ ዮሐንስም ለአባቱ ታዛዥ በመሆን ተቀብሎ ወስዶ ተከለው በየቀኑም ሁለት ሁለት ጊዜ ያጠጣዋል ውኃውም ዐሥራ ሁለት ምዕራፍ ያህል የራቀ ነው።

ከሦስት ዓመትም በኋላ ያ ዕንጨት አቈጥቊጦ በቀለ ታላቅም ዛፍ ሁኖ አብቦ ጣፋጭ ፍሬን አፈራ። አባ ባይሞይም ከፍሬው ለቅዱሳን አረጋውያን ወሰደላቸውና የታዛዡንና የትሑቱን ፍሬ እነሆ ብሉ አላቸው እነርሱም ይህን ድንቅ ተአምር አይተው አደነቁ ለመምህሮቻቸው ለሚታዘዙ እንዲህ ያለ ጸጋ የሚሰጥ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት።

አባ ባይሞይም ዐሥራ ሁለት ዓመት ያህል በጽኑዕ ደዌ ውስጥ ተይዞ ኖረ አባ ዮሐንስም ያገለግለው ነበር አባ ዮሐንስን እንደፈተነው የተመረጠ መሥዋዕትን ይሆን ዘንድ በዚህ ደዌ እንዲፈተን እግዚአብሔር ፈቅዷልና።

በሚሞትበትም ጊዜ አባ ባይሞይ ቅዱሳን አረጋውያን መነኰሳትን ሰበሰባቸውና አባ ዮሐንስንም እጁን ይዞ እርሱ ሰው ያይደለ መልአክ ነውና ተቀብላችሁ ጠብቁት ብሎ ሰጣቸው ። እርሱንም ደግሞ እንዲህ አለው ከእረፍቴ በኋላ ያን ዕንጨት ወደ ተከልክበት ቦታ በዚያ ኑር እግዚአብሔር ላንተ ያዘጋጀልህ ነውና ብዙዎችም በአንተ እጅ ይድናሉ መታሰቢያህም በዚያ ጸንቶ ይኖራል ዜናህም በዓለም ሁሉ ይወጣል ይህንንም ተናግሮ አረፈ አክብረውም ቀበሩት።

ከዚህም በኋላ ቅዱስ አባ ዮሐንስ አረጋዊ አባቱ አባ ባይሞይ እንደነገረው ወደዚያ ቦታ ሒዶ ኖረ ዜናውም በዓለም ሁሉ እጅግ እስከ ተሰማ ድረስ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ።

በራሱ ቤተ ክርስቲያንም አበ ምኔት ሁኖ ተሾመ በሹመቱም ጊዜ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ እጆቹን በራሱ ላይ ሲጭን አክዮስ አክዮስ አክዮስ የሚል ቃል ከሰማይ ተሰማ ይህም ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል ማለት ነው ። የቊርባን ቅዳሴን በሚቀድስ ጊዜ ቅዱስ ቁርባንን መቀበል የማይገባቸውን ይለያቸዋል ዛሬስ ሒዳችሁ ንስሓ ግቡ ከዚያም በኋላ ተመልሳችሁ ሥጋውን ደሙን ተቀበሉ ይላቸዋል።

ይህን አባ ዮሐንስንም ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ የቅዱሳን የሠለስቱ ደቂቅን ሥጋቸውን እንዲአመጣለት ወደ ባቢሎን ልኮታል ይህም በግንቦት ወር በዐሥረኛው ቀን ተጽፎአል ። በአንዲትም ዕለት አንድ መነኰስ ሊጎበኘው ወደ በዓቱ ቢመጣ አባ ዮሐንስን ተኝቶ አገኘው የእግዚአብሔርም መላእክት በላዩ ይጋፉ ክንፎቻቸውንም ያርገበግቡ ነበር አንዱም ሌላውን ተወኝ ክንፌን በላዩ ላኑር ይለዋል ይህንንም አይቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው ።

ከዚህም በኋላ የመነኩሳቱን መንደር ሊበረብሩ የበርበር አረማውያን ወደ አስቄጥስ ገዳም በመጡ ጊዜ አባ ዮሐንስም ወደ አባ እንጦንስ ገዳም ወደ ቁልዝም ሔደ በዚያም በአባ እንጦንስ ገዳም በጎኑ በአለ ቦታ ተቀመጠ እስከ ሚያርፍባትም ቀን ድረስ የሚያገለግለው አንድ የታመነ ሰውን እግዚአብሔር አመጣለት ።

ከዚህም በኋላ ከዚህ ዓለም ድካም ሊአሳርፈው በወደደ ጊዜ እግዚአብሔር ቅዱሳን ጻድቃኖቹን አባ እንጦንስን፣ አባ መቃርስን፣ አባ ጳኵሚስን ከእርሳቸውም ጋር መንፈሳዊ አባቱ አባ ባይሞይን ያረጋጉትና ከዚህ ከኃላፊው ዓለም መለየቱን ይነግሩት ዘንድ ወደርሱ ላካቸው ። እነርሱም እንዲህ ብለው አረጋጉት ደስ ይበልህ እግዚአብሔር የማያልቅ ተድላ ደስታን አዘጋጅቶልሃልና ክብር ይግባውና ጌታችንም እንዳዘዘ በእሑድ ቀን ሁለተኛ ወዳንተ መጥተን ወደ ዘላለም ሕይወት እንወስድኻለን ባርከውትም ከእርሱ ዘንድ ተመለሱ ።

በዐርብ ቀንም አገልጋዩን ወደ አንድ ቦታ ላከው ከዚህም በኋላ ጥቂት ታመመ በእሑድም ቀን ሌሊት ዶሮ ሲጮህ እሊያ ቅዱሳን ከሁሉም ቅዱሳን ማኅበር ጋር መጡ የመላእክትም ሠራዊት ሁሉ ወደርሱ መጡ በአያቸውም ጊዜ ደስ ብሎት በእግዚአብሔር እጅ ነፍሱን ሰጠ መላእክትም እያመሰገኑና እየዘመሩ በታላቅ ክብር ነፍሱን አሳረጓት በዚያንም ጊዜ ረድኡ መጣ ነፍሱንም ከበው እያመሰገኑ ሲያሳርጓት የጻድቃንና የመላእክትን ማኅበር አይቶ እያደነቀ አንድ ሰዓት ያህል ቆመ ። ከመላእክትም አንዱ ወደርሱ መጥቶ የቅዱሳንን ስማቸውን በመጥራት በጣቱ እያመለከተ ይህ አባ ዕገሌ ነው ብሎ አስረዳው ረድኡም መልአኩን እንዲህ ብሎ ጠየቀው ይህ በፊታቸው ያለ ፊቱ እንደ ፀሐይ የሚበራ ማን ነው መልአኩም የመነኰሳቱ ሁሉ አባት አባ እንጦንስ ነው ብሎ መለሰለት።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

29 Oct, 09:13


በዐመጸኛው ገንዘብ ወዳጅ አብጁ
ክፍል 1


በርእሰሊቃዉንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ



መልካም ቀን ቤተሰብ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

29 Oct, 07:20


ልባም ሴት ምን ዓይነት ናት?

፩. ልባም ሴት ራሷን ለፈጣሪዋ አሳልፋ ትሰጣለች።

፪. ልባም ሴት ለባሏ ዘውድ ነች በቤት ውስጥ እንደ እንደ አደይ አበባ ትታያለች የቤቱ ውበትም እርሷ ነች። ሁሉ ሲያት ይደሰትባታል ንግግሮችዋ በጨው የተቀመሙ ናቸው ተግባሯ የእውነተኛ ክርስቲያን ተግባር ነው።

፫. ልባም ሴት ለሐሜት ጊዜ የላትም ጊዜዋን በቃለ እግዚአብሔር፣ በጸሎት የተሞላ ነው፡፡

፬. ልባም ሴት ዓለም ላይ ያለው ልብስ ሁሉ ለሷ እንደማይመጥን ታውቃለች፤ በብልጭልጭ እና በፋሽን አትታለልም ሺህ ወንድ እሷን ፈልጎ ቢመጣ ምንም አይመስላትም ራሷን አታኮራም፣ ውበት ከንቱ ጠፊና ረጋፊ እንደሆነ ታውቃለችና።

፭. ልባም ሴት ሰውን አትንቅም ታጋሽ ነች ቁጣዋም የዘገዬ ነው፤ ለበጎ ሥራ እግሮችዋ ይሮጣሉ ንግግሯ ሁል በጨው እንደተቀመመ በቃለ እግዚአብሔር የታሸ ነው።

፯. ልባም ሴት ዕድሜዋን ሙሉ መልካም ታደርግለታለች፥ ክፉም አታደርግም።
(መፅሀፈ ምሳሌ 31 ፥ 12)

፯. ልባም ሴት ብዙ ተስፋ አላት በሚገጥማት ውጣ ውረድ አትጨነቅም ስጋትም አይገጥማትም እግዚአብሔር ከችግሮቿ በላይ ስለሆነ ችግሮችን እንደሚፈታ ታምናልች።

፰. ልባም ሴት ዝም ብላ በምድር ላይ ኖራ አታልፍም ለትውልድ የሚጠቅም ተግባር ሰጥታ ታልፋለች።

፱. ልባም ሴት ዓላማ እንደሌለው እንደ ኖህ አሞራ በወጣችበት አትቀርም፥ በጊዜ ወጥታ በጊዜ ትመለሳለች ፍሬ አልባ በለስም አይደለችም፥ በምታደርገው ነገር ሁሉ እንደ ንብ ታታሪ ነች።

፲. ልባም ሴት ከፈጣሪ የተሰጣት ጊዜ በአግባቡ ትጠቀማለች ያለ አግባቡ የሚባክን ጊዜና ሰዓት የላትም።

፲፩. ልባም ሴት ለማስታረቅ ትሮጣለች እንጂ በሰው ነገር አትገባም፤ ሰነፍ የተባለው ናባል ዳዊትን በሰደበው ጊዜ ዳዊትም ሊያጠፋው ሲሄድ ከመንገድ አቢጊያን አገኛት፥ እርሷም በትህትና ያዘችው ለመነችውም አሳቡንም አስቀየረች፥ ልባም ሴት መጥፎን በበጎ ታስቀይራለች።

፲፪. ልባም ሴት ቂም በቀልን አትይዝም ሆደ ሰፊና አርቆ አሳቢ ሁሉን እንደ አመሉ
የምታስተናግድ ትዕግስተኛ ናት።

በእውነት! "ልባም ሴት ማን ናት?"
( መፅሀፈ ምሳሌ 31 ፥ 10 - 30 ) በእርግጥም ልባም ሴት ዋጋዋ ከቀይ እንቁ ትበልጣለች። እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ውበት ሽልማት ጌጥ ናት።



ሠናይ ቀን

💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

26 Oct, 18:01


መስቀል ማለት ምን ማለት ነው ?

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

26 Oct, 17:02


🤔 የማንን መዝሙር ማዳመጥ ይፈልጋሉ⁉️

📌 ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
📌 ሊቀ መዘምራን ይልማ ኃይሉ
📌 ሊቀ መዘምራን ኪነጥበብ
📌 ዘማሪ አርቲስት ይገረም ደጀኔ
📌 ዘማሪ ገ/ዮሐንስን ገ/ፃዲቅ
📌 ቀሲስ ምንዴዬ ብርሀኑ
📌 ዘማሪት ሲስተር ህይወት ተፈራ
📌 ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ
📌 ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
📌 ዘማሪ ዲ/ን ሮቤል ማቲያስ
📌 ዘማሪት ፋሲካ ድንቁ
📌 ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን
📌 ዘማሪት አቦነሽ አድነው
📌 ዘማሪት ዶ/ር ሔለን ተስፋዬ

እና የሌሎችንም ...........

ዘማሪዎችን መዝሙሮች እና አዳዲስ
መዝሙሮችን ለማግኘት ከስር OPEN
የሚለውን ይጫኑት። 👇

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
█ ▒ ░✞ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ❖ 𝑶𝑷𝑬𝑵 ✞░ ▒ █
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

26 Oct, 10:23


ድንቅ ትምህርት!!


መ/ርአይቼዉ


💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

26 Oct, 07:59


#ዋናው_እኔ_ነኝ

ብዙ የበደሉህ ዋኖች ይኖራሉ እንደ እኔ ግን አልበደለሁም፣ አንተን ያስከፉህ ቢሰለፉ ከፊት የምገኘው
እኔ ነኝ፣ በኃጢአት ባህር መዋኘት ድሎት የሆናቸው ብዙ አሉ ዋናው ግን እኔ ነኝ፣ ልክ ባልሆነው ጎዳና የሚራመዱ አሉ መሪያቸው ግን እኔ ነኝ፣ አንተን በመቅረብ ፈንታ ጀርባ የሰጡህ አሉ እኔ ግን እብሳለሁ፣ ጌታዬ መድሃኒቴ ኢየሱስ አንተን የምትል ነፍሴ በስጋ ድካም ውስጥ ሳለ አለሁሽ ያልካት አንተ ነህ።

እኔ መማርህ እንዴት ያለ ምህረት ነው። የምህረትህ ድልድልነት ለእያንዳንዱ መንገዴ መሸጋገሪያ ሆኖኛል። እኔን ለማዳን ወደዚች አለም የመጣ አስታዋሼ አንተ ነህ። ከነ ኃጢያቴ እንዳልጠፋ እኔ ባለሁበት ተገኝተህ ያገኘኸን ፈላጊዬ ነህ፣ በሞት ጥላ ውስጥ ያለሁትን በደምህ ድምጽ የጠራኸኝ ባለውለታዬ አንተ ነህ፣ በምድረበዳው ብቻዬን ስባዝን ና ወደ እኔ ያልከኝ አስጠጊዬ አንተ ነህ።

እኔ ብቻ እንኳን በኃጢያት የጠፋው ብሆን የራስህ ጉዳይ ብለህ ከነበደሌ የማትተወኝ ለእኔ ብቻ እንኳን ብለህ ልትሞትልኝ የምትመጣ አፍቃሪዬ ነህ። ለእኔ ስትል ሰው የሆንክ አምላኬ ክርስቶስ ሆይ ክበር ተመስገን። እኔን ዋናውን ለማዳን ስትል ከሰው ተርታ ተገኝተህ በሰው ልክ የተመላለስክ ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ክርስቶስ ተመስገን።

ወደ ክብሬ ልትመልሰኝ ክብርህን እንደመቀመት ሳትቆጥር ከላይ ከሰማያት የመጣህልኝ አንተ ነህና አመሰግንሃለሁ። እኔን ከማርከኝማ እኔን ይቅር ካልከኝማ ማንም ትምራለህ። እኔን ዋናውን ከተቀበልክማ መዳፍህ ሰፊ ነው ሁሉን ይቀበላል።

ለእኔ ስለሆነው በጎነትህ ክብር ይሁንልህ። አሜን

“ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ ከኃጢአተኞችም ዋና እኔ ነኝ፤”  1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥15


በቸር ዋሉ💖
        

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

26 Oct, 07:29


​​✞ ስድቤን አርቀሽ

ስድቤን አርቀሽ ነውሬን ሸፈንሽው
እመአምላክ በአንቺ መቼም አላፍርም
ስምሽን ጠርቼ እጽናናለሁ
ሐዘኔን በአንቺ እረሳለሁ

ነውር አለብኝ ብዙ ስድብ
አንጀት የሚልጥ ልብ የሚያቆስል
ስሜን ለውጠው ቢያንቋሽሹኝ
በሐዘን በለቅሶ ድንግል መጣሁኝ
    እንደ ሃና ሆኜ በቤተ መቅደስ
    በመረረ ሐዘን ነው የማለቅስ
    ፍረጂልኛና ልመለስ ከቤቴ
    ሐዘኔን በደስታ ለውጪው እናቴ
በግራም በቀኝም ጠላት ቢከበኝ
አብዝቼ እጮሃለው እናቴ ስሚኝ

አዝ-----

መከራው በዝቶ ግራ ገብቶኛል 
ድምፅሽን ልስማ ያረጋጋኛል 
የሰው ህይወቱ ብርቱ ሰልፍ ነው      
ደስታና ሐዘን የማይለየው
    በእጃችን ወድቋል ሲሉ ጠላቶቼ
     አመለጥኳቸው ስምሽን ጠርቼ
     ሰው የዘራውን ያንኑ ያጭዳል
     በቆፈረው ጉድጓድ ራሱ ይገባል
እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ
ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ

አዝ--------

በምርኮ ሳለሁ ከሰው አገር     
ግፍ ውለውብኝ ስኖር በእስር      
ምልጃሽ ደርሶልኝ ተፈትቻለሁ      
በተአምራትሽ እኔ ድኛለሁ
     ቃልሽን ሰምቶ ጽንሱ ሰገደ
     ብላለች ኤልሳቤጥ ነውሬ የተወገደ
     የጌታዬ እናት እኔን አሰበችኝ
     ታሪኬን ቀይራ ይኸው ባረከችኝ
የእመቤቴ ከሆንኩ ማን ይቃወመኛል
ወጀቡም ማእበሉም ይታዘዝልኛል
አዝ------
ወይንኮ አልቋል የዶኪማስ ቤት      
ድንግል አማልጅው ነይ የእኛ እመቤት      
ስምሽ ሲጠራ በየቦታው      
ይመላልና የጎደለው           
   ግራ የገባው የቸገረው            
    ድንግልን ይጥራት እንድትረዳው            
     ሳዝን ስተክዝ የምታጽናና            
     እናት አለችኝ ርኅርኂተ ልቦና
እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ
ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

26 Oct, 03:55


በግራኝ አሕመድ ወረራ ወቅት የግራኝ ሠራዊት አብያተ ክርስቲያናቱን እናጠፋለን ብለው ሲመጡ በተኣምራት ሰምጠው እንደጠፉ አባቶች ያስረዳሉ። አዛዦቹንም በዋሻ ውስጥ የሚገኙት ወፍ የሚያህሉ ተርቦች ነድፈው ጨርሰዋቸዋል። እነዚያ ተርቦች አሁንም ድረስ በገዳሙ ውስጥ ያልተፈቀደ ነገር ሲደረግ በመናደፍና በመከልከል ዋሻውን የሚጠብቁ ሲሆኑ አንዱ ተርብ ከነደፈ ሕይወት ሊያጠፋ እንደሚችል የገዳሙ አባቶች ይናገራሉ። ከዚኸም በላይ ዋሻው በነብርም ይጠበቃል።

ገዳሙ ባለብዙ ቃልኪዳን ሲሆን ብዙ ስውራን አበው ዛሬም የሚኖሩበት ትንቢታቸው የማይነጥብ ብዙ ግሁሳን የከተሙበት ነው። ስውራኑ አበው ዛሬም እግዚአብሔር ለፈቀደለት ሰው ይገለጣሉ። ደገኞቹ የኢትዮጵያ ቀደምት ነገሥታት የገዳሙን ክብር በመረዳት ቦታው ድረስ በመሔድ በረከት ይቀበሉ ነበር። ዳግማዊ ምኒሊክ ለጀር ሥላሴ ገዳምና ለገዳማውያኑ አለኝታ ስለነበሩ በገዳሙ የታሪክ መዝገብ ስማቸው ዘወትር ይነሳል። ግርማዊ ዐፄ ኀይለ ሥላሴ ቦታውን ይንከባከቡት የነበረ ሲሆን ለገዳሙ መርጃ የሚሆን አዲስ አበባ ላይ የሚከራይ ቤት አሠርተው በኪራዩ ገቢ ገዳሙ እንዲጠቀም አድርገው ነበር። በአካልም ገዳሙ ድረስ በመሔድ በረከትን ይቀበሉ ነበር።

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ጥቅምትና #ከገድላት_አንደበት)

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

26 Oct, 03:55


#ጥቅምት_16

አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
ጥቅምት ዐሥራ ስድስት በዚች ቀን የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት #አባ_ያቃቱ አረፈ፣ የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም እረድዕ የነበሩት #አቡነ_ኢያሱ_ዘጀር_ሥላሴ በዓለ ዕረፍታቸው ነው።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#ቅዱስ_አባ_ያቃቱ

ጥቅምት ዐሥራ ስድስት በዚች ቀን ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ዘጠነኛ የሆነ ቅዱስ አባት የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ያቃቱ አረፈ።

ከርሱ በፊት የነበረ አባ ብንያሚን በአረፈ ጊዜ ይህን አባት መርጠው በእስክንድርያ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾሙት በዘመኑም ብዙ ችግር ደርሶበታል ስሙ ቴዎዶስዮስ የሚባል አንድ መለካዊ ሰው ነበረ እርሱም ወደ ደማስቆ ንጉሥ ወደ ዘይድ ሒዶ ብዙ እጅ መንሻ ሰጥቶ ለእስክንድርያ አገረ ገዥ ሁኖ ተሾመ።

ይህንንም አባት አባ ያቃቱን ሊአስጨንቀው ጀመረ በየዓመቱ ግብር ሰባት ሺህ የወርቅ ዲናር ከእርሱ እስከተቀበለ ድረስ እግዚአብሔርም እስከ አጠፋው ድረስ ይህን አባት እንዲህ አሠቃየው።

በዘመኑም የብዙዎች ቅዱሳን አባቶች አባት የሆነ የአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ሕንፃዋ ተፈጸመ።

በአንዲት ሌሊትም ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ለዚህ አባት ተገለጸለት ፍዩም በሚባል አገር በአባ መቃርስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያገለግል ዮሐንስ የሚባል ጻድቅ ሰው መነኰስ እንዳለ ነገረው። ሕዝብን በማስተማርና በመምከርም ይረዳው ዘንድ መልእክተኞችን ልኮ እንዲአስመጣውም አዘዘው ሁለተኛም ከእርሱ በኋላ ሊቀ ጳጳሳት እንደሚሆን ገለጠለት።

በዚያንም ጊዜ መልእክተኞችን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሥራውንም ሁሉ አስረከበው ይህንንም አባት ከብዙ ድካም የሚያሳርፈው ሆነ በሹመቱ ወንበር ዐሥራ ዘጠኝ ዓመት ኑሮ ከዚህም በኋላ በሰላም አረፈ።

✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞

#አቡነ_ኢያሱ_ዘጀር_ሥላሴ

አቡነ ኢያሱ በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በሰሜን ሸዋ የተነሡ ሲሆን ምንኵስናቸውን ከደብረ ሊባኖሱ ከዕጨጌ አቡነ መርሐ ክርስቶስ እንደተቀበሉ ታሪካቸው ያስረዳል። ትውልዳቸው አምሐራ ሳይንት ሲሆን መካነ ሱባኤ ወተመስጦ ጀር ቅድስት ሥላሴ ገዳምን የመሠረቱ ታላቅ ጻድቅ ናቸው።

እርሳቸው የመሠረቱት ጀር ቅድስት ሥላሴ ገዳም በግራኝ ወረራ ሳይወድም ስለቀረ ጥንታዊነቱን እንደጠበቀ ስለሚገኝና ታላቅ የበረከት ቦታ የቅዱሳን መናኸሪያ ስለሆነ ብዙዎች ነገሥታት ገዳሙን እየሔዱ ተሳልመው በረከት አግኝተውበታል። የአቡነ ኢያሱን ገድላቸውን ከአቡነ ሀብተ ማርያም ገድል ጋር ጣልያናዊው ራይኔሪ በሀገሩ ሮም እንዳተመው ቀሲስ ዶ/ር አምሳሉ ተፈራ ጽፈዋል። (0s valdo Raineri, Atti di Habta Māryam (†1497) e.di Iyasu (†1508), Santi Monaci Etiopici, Roma 1990 (Or ChrA 235), 165-265.)

የጻድቁ በዓለ ዕረፍታቸው ጥቅምት 16 በገዳሙ በታላቅ ድምቀት የሚከበር ሲሆን ስለ ጻድቁ ገድል በዝርዝር ተጽፎ አላገኘንም፣ ይልቁንም አቡነ ኢያሱ ስለገደሙት ታላቁ ጀር ቅድስት ሥላሴ ገዳም ነው በብዛት የሚነገረው።

አቡነ ኢያሱ ጀር ስላሴ ከመምጣታቸውም በፊት አስቀድመው በአቡነ ዜና ማርቆስ ገዳም፣ በደብረ ሊባኖስ እና በሌሎችም ገዳማት እየተዘዋወሩ በተጋድሎ ሲቀመጡ ‹‹ቦታኸ ይኸ አይደለም›› ተብለው በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ነው ወደ ጀር ሥላሴ የመጡት። ወደ ቦታው ከመምጣታቸው በፊት አካባቢው ባእድ አምልኮ የተስፋፋበት ነበር፣ ነገር ግን ጻድቁ ሕዝቡን ክርስትናን አስተምረው ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሰውታል። የምንኵስናን መሠረት ጥለውበታል። የአቡነ ኢያሱ የዕረፍታቸው ቦታ ደብረ ሊባኖስ ቢሆንም መታሰቢያቸው በመራቤቴ በሚገኘው አስደናቂ ገዳማቸው ይታሰባል። በገዳሙ በክብረ በዓሉ ወቅት ታቦት አይወጣም፣ ከበሮ አይመታም። ምክያቱም ፍጹም የጸሎት የጽሞና ቦታ ስለሆነ ነው።

መካነ ሱባኤ ወተመስጦ ጀር ቅድስት ሥላሴ አቡነ ኢያሱ ገዳም በተፈጥሮአዊ አቀማመጡ እጅግ አስደናቂ ሲሆን በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ በደንቢ ግራርጌ ቀበሌ ጀር በሚባል ስፍራ የሚገኝ ታላቅ ገዳም ነው። ገዳሙ ከአዲስ አበባ 137 ኪ.ሜ ከደብረ ብርሃን 91 ኪ.ሜ ከለሚ ከተማ 4 ኪ.ሜ ርቀት ላይ የሚገኝ ከጥንት ጀምሮ ስዉር ገዳም ሆኖ የቆየ ነው። ገዳሙ በ1495 ዓ.ም በዐፄ ናኦድ ዘመነ መንግሥት በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ጻዲቁ አቡነ ኢያሱ ወደዚህ ቦታ መጥተው መሥርተውታል። በጅረት ታጂቦ ስለሚገኝ ነው ጀር ሥላሴ የተባለው። የክብር ባለቤት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በራእይ አስመልክቶ ከመሠረታቸው ገዳማት አንዱ ነው። አቡነ ኢያሱም በገዳሙ በሚገኘው አንድ ትልቅ ዋርካ ሥር ቆመው ይጸልዩ እንደነበር አባቶች ያስረዳሉ። አሁንም ድረስ ዋርካው በሥፍራው ላይ ሕያው ማስረጃ ሆኖ ይገኛል።

ገዳሙ ከአቡነ ኢያሱ ዕረፍት ከዘመናት በኋላ በግራኝ አህመድ ወረራ ጥቃት ደርሶበት መነኰሳቱም ተበታትነው ለ247 ዓመት ጠፍ ሆኖ ከቆየ በኋላ በ1747 ዓ.ም አቡነ ዮሴፍ የተባሉት ጻድቅ በሊቀ መላእክት በቅዱስ ሚካኤል መሪነት ከአምባሰል ተነሥተው መጥተው ገደሉን ቦርቡረው ቅኔ ማሕሌት፣ ቅድስትና ቅዱሳንን ያሟላ ቤተ መቅደስ በማነጽ ዳግም ገዳሙን በማቅናት የቀደመውን የአባቶችን ታሪክ ማስቀጠል ችለዋል። በግራኝ አህመድ ወረራ ወቅት ቅርሶቹና ነዋየ ቅዱሳቱ አደጋ እንዳይደርስባቸው አባቶች ሰብስበው በስውር ከቀበሩ ከረጅም ጊዜ በኋላ የቀበሩበት ቦታ ጠፍቶባቸው ነበር ነገር ግን የወንዙ ውኃ አቅጣጫውን ቀይሮ ሽቅብ ፈስሶ ቅርሶቹ ያሉበትን ቦታ አመላክቷል።

መካነ ሱባኤ ወተመስጦ ጀር ቅድስት ሥላሴ አቡነ ኢያሱ ገዳም የበርካታ መናንያን አበው በኣት ከመሆኑም ባሻገር የወንዶች ብቻ ገዳም ሲሆን መናንያኑ ከአራዊት ጋር ተስማምተው የሚኖሩበት ነው። ዙሪያው በገደል የተከበበ ሲሆን ወደ ገዳሙ ለመውረድ የዕንጨት መሰላልን ተጠቅሞ መጓዝ ግድ ይላል። ወደ ገዳሙ መግቢያ የሚያስወርደው መሰላል ደቡብ ወሎ ከሚገኘው ከታላቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ገዳም መግቢያ ጋር ይመሳሰላል። የመሰላሉ ርዝመት ከ15 ሜትር በላይ ይሆናል።

ገዳሙ ከእግዚአብሔር ጋር በሱባዔ ለመገናኘት ፍጹም ጸጥታ የሰፈነበት ከመሆኑም በላይ ረድኤተ እግዚአብሔር ያለበት ቅዱስ ቦታ ነው። ዋሻው የሚከፈተው ዐቢይ ጾም ላይ እና በእመቤታችን የፍልሰታ ጾም ወቅት ነው። በዋሻው ውስጥ ሱባዔ የሚያዘው በደረቅ ሽምብራ ቆሎ እና በአንድ ኩባያ በሶ ብቻ ነው። አባቶች በኣት ዘግተው ጾመ ፍልሰታን፣ ጾመ ነቢያትን፣ ጾመ ሐዋሪያትን በይበልጥ በምነና ሕይወት የሚያሳልፉበት የበረከት ገዳም ነው።

በጀር ሥላሴ የሚገኘው ታሪካዊ ታላቅ ተራራ በልበሊት ኢየሱስን ግራኝ አሕመድ ሲያቃጥል ሁለት በወርቅ የታነጹ አብያተ ክርስቲያናት በፍቃደ እግዚአብሔር እንደሰወረ አባቶች ይናገራሉ። ይኸም ጥንታዊና ታሪካዊ ተራራ አሁንም በቦታው የሚገኝ ሲሆን በዋሻው ውስጥ የክብር ባለቤት ጌታችን በስደቱ ወራት ከእናቱ ድንግል ማርያም፣ ከዮሴፍና ከሰለሜ ጋር ለጥቂት ጊዜ የተቀመጠበት ሲሆን አቡነ ዜና ማርቆስና አቡነ ተክለ ሃይማኖትም በምነና የተጋደሉበት ታላቅ ዋሻ ነው። ዋሻው እስከ ኢየሩሳሌም ድረስ ውስጥ ለውስጥ የሚያስኬድ ሲሆን በውስጡ ከ40 በላይ አብያተ ክርስቲያናት እንደተሰወሩበት አባቶች ይናገራሉ።

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

25 Oct, 07:55


በዋጋ ገዝተኸኛልና

በዋጋ ገዝተኸኛልና
ስለ እኔ ደም ከፍለሀልና/2/
ልሳኔ ያውጃል ክብርህን
አልረሳም ጌታ ውለታህን/2/
አዝ
ህይወት ሠላምን ትቼ
የማይታይ አይቼ
ላንተ ብሰጥ ጀርባዬን
ልተዋወቅ ጠላቴን
የጠበቀኝ ውጊያ ነው
የተረፈኝ ፀፀት ነው
የሻረልኝ ቁስለቴ
ተሰቅለህ ነው አባቴ
አዝ
እጓዛለሁ በምናብ
ወደ ሠላሜ ወደብ
እጄን በአፌ እጭናለሁ
ዛሬም እፁብ እላለሁ
ለክብርህ መሠለፌ
በለምለሙ ማረፌ
ዋጋ ከፍለህ ነው ጌታ
ያኖርከኝ በፀጥታ
አዝ
ከወሃ ከመንፈስ
ተወልጄ በመቅደስ
ልጅህ ሆንኩኝ ዳግመኛ
የመስቀልህ ምርኮኛ
በአንተ ስለመዳኔ
ምስክርህ ነኝ እኔ
ላይታጠፍ ምላሴ
እቀኛለሁ በነፍሴ

ዘማሪ ገብረዮሐንስ ገብረፃዲቅ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Oct, 21:20


✝️ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞


✞ እንኳን ለአባቶቻችን ቅዱሳን "12ቱ ሐዋርያት" እና ለቅዱስ "ቢላሞን ሰማዕት" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞


ቅዱሳን 12ቱ ሐዋርያት

=>በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከእመቤታችን በቀር ከቅዱሳን ሐዋርያት የሚበልጥ አልተነሳም:: "ሐዋርያ" ማለት "ፍንው: ልዑክ: የተላከ: የጽድቅ መንገደኛ" እንደ ማለት ነው:: በምሥጢሩ ግን "ባለሟል" ብለው ሊቃውንቱ ተርጉመውታል::

† ይህስ እንደምን ነው ቢሉ:-

¤የፍጥረታት ሁሉ ጌታ: የክብር ባለቤት መድኃኔ ዓለም ከድንግል ማርያም ተወልዶ: አድጐ: ተጠምቆ: ጾሞ: ከገዳመ ቆረንቶስ ሲመለስ ቀዳሚ ሥራው ያደረገው ደቀ መዛሙርቱን መጥራት ነበር::

+ከተከተሉት የ5 ገበያ ሕዝብ መካከል "ወሐረየ እምሰብአ ዚአሁ አሠርተ ወክልኤተ ሐዋርያተ" እንዲል በመጀመሪያ 12ቱን ሐዋርያት መረጠ::

✝️ እሊህም:-

1.ዼጥሮስ የተባለ ስምኦን
2.እንድርያስ (ወንድሙ)
3.ያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
4.ዮሐንስ (ወንድሙ)
5.ፊልዾስ
6.በርተሎሜዎስ
7.ቶማስ
8.ማቴዎስ
9.ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ
10.ታዴዎስ (ልብድዮስ)
11.ናትናኤል (ቀናተኛው ስምዖን) እና
12.ማትያስ (በይሁዳ የተተካ) ናቸው:: (ማቴ. 10:1)

+እነዚህን 12 አርድእቱን ከጠራ በሁዋላ ለ3 ዓመታት ከ3 ወራት ከዋለበት ሲማሩ ይውሉ ነበር:: ሌሊት ደግሞ ምሥጢር ሲያስተረጉሙ ያድሩ ነበር::

+ጌታ እንደሚገባ ካስተማራቸው በሁዋላ ከፍ ያለ ኃላፊነትን ሾማቸው:: ለዓለም እረኞች: የእርሱም ባለሟሎች ሆኑ:: እጅግ ብዙ መከራ እንደሚገጥማቸው ነገራቸው:: (ማቴ. 10:16, ዮሐ. 16:33) በዚያው ልክ ክብራቸውንም አከለላቸው:: (ማቴ. 19:28)
+ሥልጣናቸው ደግሞ እስከዚህ ድረስ ሆነ:: "በምድር ያሠራችሁት በሰማይ የታሰረ ይሆናል: በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይሆናል::" (ማቴ. 18:18) "ይቅር ያላችሁዋቸው ኃጢአታቸው ይቀርላቸዋል: ያላላቹሃቸው ግን አይቀርላቸውም::" (ዮሐ. 20:23)

+የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ (ማቴ. 16:19): እረኝነትን (ዮሐ. 21:15) ተቀበሉ:: ጌታ በንጹሕ አንደበቱ ሐዋርያቱን እጅግ ሲያከብራቸው "ጨው: የዓለም ብርሃናት" (ማቴ. 5:13) አላቸው:: ወንድሞቹም ተባሉ:: (ዮሐ. 7:5) ከዚህም በሚበልጥ በሌላ ክብር አከበራቸው::

+ከዚህ ሁሉ ነገር በሁዋላ በጌታ ሕማማት ጌዜ ገና ነበሩና አንዳንዶቹ ፈርተው ተበተኑ:: ተመልሰው ግን በጽርሐ ጽዮን ሲጸልዩ ሰንብተው የጌታን ትንሳኤ ተመለከቱ:: እጆቹን: እግሮቹንም ዳስሰው ሐሴትን አደረጉ::

+ለ40 ቀናት መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓት: ሌላም በፍጡር አንደበት የማይነገር ብዙ ምሥጢራትን ተምረው: ጌታ ሊቀ ዽዽስናን ሹሟቸው ዐረገ::

+ለ10 ቀናት በእመ ብርሃን ሥር ተጠልለው ሲጸልዩና በአንድ ልብ ሲተጉ ሰንብተው መንፈስ ቅዱስ ወረደላቸው:: በአንዴም ከፍርሃት ወደ ድፍረት ተመልሰው ፍጹማን: ብርሃናውያን ሆኑ:: 71 ልሳናትን ነስተው በአንዲት ስብከት ብቻ 3ሺ ነፍሳትን ማረኩ:: (ሐዋ. 2:41)

+ቅዱሳን ሐዋርያት በኅብረት ለአንድ ዓመት ያህል በኢየሩሳሌምና በዙሪያዋ እየተመላለሱ አስተምረው ብዙ እሥራኤላውያንን ወደ ክርስትና ማርከዋል:: ከዚህ በሁዋላ ግን እንደ ትውፊቱ በዚህች ቀን ዓለምን በእጣ ለ12 ተካፈሏት::

+ይህ ሲሆን መንፈስ ቅዱስ አብሯቸው ነበርና ለእያንዳንዳቸው እንደሚገባቸው አሕጉረ ስብከቶች ደረሷቸው:: እነርሱም ደቀ መዛሙርቶቻቸውን አስከትለው ለታላቁ መንፈሳዊ ዘመቻ ወረዱ::
+በሔዱበት ቦታም ከተኩላ: ከአንበሳና ከነምር ጋር ታገሉ:: በጸጋቸውም አራዊትን (ክፉ ሰዎችን) ወደ በግነት መልሰው ለክርስቶስ አስረከቡ:: በየሃገሩ እየሰበኩ ድውያንን ፈወሱ:: ለምጻሞችን አነጹ:: እውራንን አበሩ:: አንካሶችን አረቱ:: ጐባጦችን አቀኑ:: ሙታንንም አስነሱ:: እልፍ አእላፍ አሕዛብንም ወደ መንጋው ቀላቀሉ::

+ስለዚህ ፈንታም ብዙዎቹ በእሳት ተቃጠሉ:: ቆዳቸው ተገፈፈ:: በምጣድ ተጠበሱ:: ደማቸው በምድር ላይ ፈሰሰ:: ከአንድ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በቀር ሁሉም ይህችን ዓለም በሰማዕትነት ተሰናበቱ:: ጨው ሆነው አጣፍጠዋልና: ብርሃንም ሆነው አብርተዋልና እናከብራቸዋለን:: "አባቶቻችን: መምሕሮቻችን: ጌቶቻችንና ሊቆቻችን" እንላቸዋለን::

ቅዱስ ቢላሞን ሰማዕት

=>በዘመነ ሰማዕታት የነበረው ቅዱስ ቢላሞን በወቅቱ ይታወቅ የነበረው በክርስቲያንነቱ ሳይሆን በፈላስፋነቱ ነበር:: እጅግ የተማረ ጥበበኛ: ግን ደግሞ ወገኑ ከኢ-አማንያን በመሆኑ ክርስቶስን አያውቀውም ነበር::

+እግዚአብሔር ግን እንዲጠፋ አልፈቀደምና አንድ ካህንን ላከለት:: ከመቀራረብ የተነሳ ብዙ ስለተነጋገሩ ቢላሞን ወደ ክርስትና እየተሳበ ሔደ:: በመጨረሻም ተምሮ በካህኑ እጅ ተጠምቁዋል:: ቀጥሎም ይጾም: ይጸልይ: ይጋደል ነበር::

+በትንሽ ጊዜም ከጸጋ ደርሶ ድውያንን ይፈውስ ገባ:: ብዙ አሕዛብን እያስተማረ: ከደዌአቸውም እየፈወሰ ወደ ክርስትና መለሳቸው:: አንድ ቀን ግን "ዐይነ ሥውር አብርተሃል" በሚል ተከሶ ሞት ተፈረደበት::

+ከመገደሉ በፍትም ጌታችን ከሰማይ ወርዶ "ወዳጄ!" ሲለው ወታደሮች ሰሙ:: በዚህ ምክንያት አምነው በዚህች ቀን 158 ወታደሮች አብረውት ተሰይፈዋል::

=>አምላከ ቅዱሳን ሐዋርያት ቸርነቱን: ምሕረቱን ያብዛልን:: በምልጃቸው ሃገራችንን ከክፉ ጠብቆ ከበረከታቸው ይክፈለን::

ጥቅምት 15 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት

1."12ቱ" ቅዱሳን ሐዋርያት
2.ቅዱስ ቢላሞን ሰማዕት
3."158" ሰማዕታት (የቅዱስ ቢላሞን ማሕበር)
4.ቅዱስ ሲላስ ሐዋርያ
5.ቅድስት ጾመታ

ወርሐዊ በዓላት

1.ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ
2.ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ (አፈ በረከት)
3.ቅዱስ ሚናስ ግብፃዊ
4.ቅድስት እንባ መሪና
5.ቅድስት ክርስጢና

=>"በዚያን ጊዜ ዼጥሮስ መልሶ:- 'እነሆ እኛ ሁሉን ትተን ተከተልንህ:: እንኪያስ ምን እናገኝ ይሆን?' አለው:: ጌታ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው:- 'እውነት እላቹሃለሁ! እናንተስ የተከተላችሁኝ በዳግመኛ ልደት: የሰው ልጅ በክብሩ ዙፋን በሚቀመጥበት ጊዜ እናንተ ደግሞ በአሥራ ሁለቱ የእሥራኤል ነገድ ስትፈርዱ በአሥራ ሁለት ዙፋን ትቀመጣላችሁ:: "(ማቴ. 19:27)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር [ዲ/ዮርዳኖስ አበበ]

@degnitKindness

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Oct, 08:53


✝️ቅንነትንጉሥ ሰሎሞንን ለማየት ዉጡ



በርእሰ ሊቃዉንት አባ ገብረኪዳን ግርማ ❤️🙏


ሠናይ ቀን ቤተሰብ 💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

24 Oct, 07:29


እኔ አባታችሁና መምህራችሁ ነኝ፥ ሁላችሁ ልጆቼ ትእዛዜን አዳምጡ፤ በቅድስት ሥላሴ ማመንን እንድትከተሉና እንድትጸኑ እነግራችኋለሁና፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ እርስ በእርሳችሁ በእውነተኛ ፍቅር ትዋደዱ ዘንድ እለምናችኋለሁ።

የተወደዳችሁ ልጆቼ በፍጹም ሰብአዊነት መልካምን አንድታደርጉ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ ዓለም እንድታታልላችሁ አትፍቀዱላት፤ በእግዚአብሔር አገልግሎት ዳተኞችና ቸልተኞች አትሁኑ ብዬ እለምናችኋለሁ።

የተወደዳችሁ ልጆቼ ያለማቋረጥ እና ያለ መታከት እንድትጸልዩ እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ መለያየትን ከሚያመጣ ንግግር አንደበታችሁን እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።

የተወደዳችሁ ልጆቼ የተጠመቃችሁባትን ቅድስቲቱን ጥምቀት እንድትጠብቋት እለምናችኋለሁ፤ የተወደዳችሁ ልጆቼ ሰውነታችሁን ለጌታ ንጹሕ አድርጋችሁ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።

ልጆቼ መብራታችሁ ፈጽሞ እንዲጠፋ አትፍቀዱ ይልቅስ ብርሃንን እንዲሰጥ እንድታደርጉት እለምናችኋለሁ፤ ልጆቼ እግዚአብሔር የሰጣችሁን ትእዛዝ እንድትጠብቁ እለምናችኋለሁ።

ልጆቼ  እግዚአብሔርን መፍራት ከእናንተ ጋር እንዲሆን እለምናችኋለሁ፤ የነገርኳችሁን ሁሉ ከጠበቃችሁ የእባቡንና የዘንዶውን ራስ ትቀጠቅጣላችሁ፤ ያልኋችሁን ካደረጋችሁ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ ብርሃናዊያን ኪሩቤል ይጠብቋችኋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ


💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Oct, 14:26


እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ያበሰራት ቅዱስ መላዕክ ማን ይባላል?

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Oct, 08:04


አሟሟቴን አሳምሪዉ!?


በማስተዋል እንከታተል

በቸሩ ዋሉ


💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Oct, 07:48


ስድቤን አርቀሽ

ስድቤን አርቀሽ ነውሬን ሸፈንሽው
እመ አምላክ በአንቺ መቼም አላፍር
ስምሽን ጠርቼ እጽናናለሁኝ
ሀዘኔን በአንቺ እረሳለሁኝ
አዝ።።።
ነውር አለብኝ ብዙ ስድብ
አንጀት የሚልጥ ልብ የሚያቆስል
ስሜን ለውጠው ቢያንቋሽሹኝ
በሀዘን በለቅሶ ድንግል መጣሁኝ
እንደ ሃና ሆኜ ከቤተ መቅደስ
በመረረ ሐዘን ነው የማለቅስ
ፍረጅልኝና ልመለስ ከቤቴ
ሐዘኔን በደስታ ለውጪው እናቴ
በግራም በቀኝም ጠላት ቢከበኝ
አብዝቼ እጮሃለው እናቴ ስሚኝ
አዝ።።።
መከራው በዝቶ ግራ ገብቶኛል 
ድምፅሽን ልስማ ያረጋጋኛል 
የሰው ህይወቱ ብርቱ ሰልፍ ነው      
ደስታና ሐዘን የማይለየው
በእጃችን ወድቋል ሲሉ ጠላቶቼ
አመለጥኳቸው ስምሽን ጠርቼ
ሰው የዘራውን ያንኑ ያጭዳል
በቆፈረው ጉድጓድ ራሱ ይገባል
እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ
ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ
አዝ
በምርኮ ሳለሁ በሰው ሀገር     
ግፍ ውለውብኝ ስኖር በእስር      
ምልጃሽ ደርሶልኝ ተፈትቻለሁ      
በታምራትሽ እኔ ድኛለሁ
ቃልሽን ሰምቶ ጽንሱ ሰገደ
ብላለች ኤልሳቤጥ ነውሬ ተወገደ
የጌታዬ እናት እኔን አሰበችኝ
ታሪኬን ቀይራ ይኽው ባረከችኝ
የእመቤቴ ከሆንኩ ማን ይቃወመኛል
ወጀቡም ማእበሉም ይታዘዝልኛል
አዝ።።።።
ወይን እኮ አልቋል የዶኪማስ ቤት      
ድንግል አማልጅው ነይ የእኛ እመቤት      
ስምሽ ሲጠራ በየቦታው      
ይሞላልና የጎደለው           
ግራ የገባው የቸገረው            
ድንግልን ይጥራት እንድትረዳው            
ሳዝን ስተክዝ የምታጽናና            
እናት አለችኝ እርህርህይተ ልቦና
እናቴ እመቤቴ ብዬ ስጠራሽ
ከመከራ ሁሉ ታወጪኛለሽ

ዘማሪ ቀሲስ እንግዳወርቅ በቀለ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Oct, 07:36


🔔 ከመምህራን የማንን ትምህርት ማግኘት ይፈልጋሉ?👇

┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ምሕረተአብ አሰፋ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዘበነ ለማ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ሄኖክ ኃይሌ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዮርዳኖስ አበበ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ያረጋል አበጋዝ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር እዮብ ይመኑ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር ገብረ እግዚአብሔር
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛

🔗የሁሉንም መምህራን ትምህርት ለማግኘት🔔
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Oct, 03:26


+በነዚህ ዓመታት ሁሉ ይህ አካሉ የተለወጠ ሕጻን ቅዱስ ዘካርያስ መሆኑን ያወቀ የለም:: እንዲህ የቆሰለውም አሲድነት ካለው የጉድጉዋድ ውሃ ውስጥ ሰጥሞ ለ40 ቀናት በመጸለዩ ነው::

+በመጨረሻ ግን አባቱ በምልክት ለይቶት አለቀሰ:: "ልጄ! አንተ ለእኔ አባቴ ነህ" ብሎታል:: አበው መነኮሳትም ተሰብስበው እጅ ነስተውታል:: በ7 ዓመቱ የመነነው አባ ዘካርያስ በ52 ዓመቱ በዚህች ቀን ዐርፎ በክብር ተቀብሯል::

=>አምላከ አፈ ወርቅ ዮሐንስ የድንግል እመ ብርሃንን ፍቅሯንና ውዳሴዋን ይግለጽልን:: ከአባቶቻችን ክብርና በረከትንም ያሳትፈን::

ጥቅምት 13 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት


1.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
2.አባ ዘካርያስ ገዳማዊ
3.አባ ማርዳሪ ጻድቅ
4.ቅዱስ አብጥማዎስ ሰማዕት

ወርኀዊ በዓላት

1.እግዚአብሔር አብ
2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት
3."99ኙ" ነገደ መላዕክት
4.ቅዱስ አስከናፍር
5."13ቱ" ግኁሳን አባቶች
6.ቅዱስ አርሳንዮስ ጠቢብ ገዳማዊ
7.አቡነ ዘርዐ ቡሩክ

=>"እናንተ የምድር ጨው ናችሁ . . . እናንተ የዓለም ብርሃን ናችሁ:: በተራራ ላይ ያለች ከተማ ልትሠወር አይቻላትም:: መብራትንም አብርተው በዕንቅብ በታች አይደለም እንጂ በመቅረዙ ላይ ያናሩታል:: በቤት ላሉት ሁሉም ያበራል:: መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ::"(ማቴ. 5:13-16)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር [ዲ/ዮርዳኖስ አበበ]

@degnitKindness

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

23 Oct, 03:26


✝️ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞


❖ ጥቅምት ፲፫ (13) ❖


✞ እንኳን ለዓለም ሁሉ መምሕር "ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ" እና ለአባ "ዘካርያስ ገዳማዊ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞


ዮሐንስ አፈ ወርቅ

=>ለቤተ ክርስቲያን የብርሃን ምሰሶ ስለሆነላት ስለ ታላቁ ሐዋርያዊ ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? እንደ እኔ ያለ ኃጥእ: ለባሴ ሥጋና ገባሬ ንስሃ ስለሱ ሊናገር አይቻለውምና:: አባቶቻችን እንደ ነገሩን ስለ አፈ ወርቅ ለመናገር "አፈ ወርቅ" መሆን ያስፈልጋል:: እስኪ በቅዱሱ አባት ምልጃ ጥቂት ልሞክር::

ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ማን ነው?

=>ነገዱ ከሶርያ: የተወለደው በ347 ዓ/ም በእስክንድርያ ሲሆን አባቱ አስፋኒዶስ እናቱ ደግሞ አትናስያ ይባላሉ:: እነርሱ ደግ ቢሆኑ ይህንን እንቁ ልጅ እግዚአብሔር ሰጣቸው:: ዮሐንስ ለክርስቲያን እንደሚገባ በትምሕርትና በጥበብ አደገ:: ገና በሕጻንነቱ ወደ ግሪክ ሔዶ የዘመኑን ሳይንስ (ፍልስፍና) ከአፉ እስከ ገደፉ ተምሮ ተመልሷል::

+ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅን ለየት ከሚያደርጉት ነገሮችም አንዱ ይሔው ነው:: በዘመናዊም ሆነ በመንፈሳዊ ትምሕርት ይህ ቀረህ የማይሉት ሊቅ የሆነው ገና በ15 ዓመቱ ነበር:: በ2 ወገን የተሳለ ሰይፍ በመሆኑ ስንኩዋን በሕይወተ ሥጋ እያለ ዛሬም ለንፉቃን ትልቅ የራስ ምታት ነው::

+ቅዱሱ ገና በ16 ዓመቱ ሃብት: ንብረት: ውበት: ክብርና እውቀት የሞላለት ቢሆንም ያለውን ሁሉ ለነዳያን ሰጥቶ መጻሕፍትን ብቻ ሰብስቦ ከባልንጀራው ቅዱስ ባስልዮስ ጋር በርሃ ገባ:: ሰውነቱን በጾምና በጸሎት እየቀጣ በበርሃ ሲኖር ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስና ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ወደ እርሱ መጡ:: ሊቀ ሐዋርያት የመንግስተ ሰማያትን መክፈቻ ስልጣን ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ወንጌሉን ሰጥተው ተሰወሩት::

+ከዚህች እለት በሁዋላ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ባሕረ ምስጢራት ሆነ:: ብሉይ ከሐዲስ: ከኦሪት ዘፍጥረት እስከ ራዕየ ዮሐንስ ድረስ በአንድምታ ትርጉዋሜ ተነተናቸው:: በተለይ ሐዲስ ኪዳንን እየመላለሰ አመሰጠረው:: ቅዱስ ሕሊናው ሳይታክት: ንጹሕ እጆቹ ሳይዝሉ የጻፋቸው ድርሳናት: መልዕክታትና ትርጉዋሜያት ቢቆጠሩ አሥር ሺህ ሞሉ:: በእውነት ለዚህ አንክሮ ይገባል! የሚገርመው ይህን ሁሉ ሲሰራ እድሜው ገና ለጋ: ማዕርጉም ዲቁና ነበር::

+ከዚህ በሁዋላ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ቅስና ተሹሞ በስብከተ ወንጌል ብዙ ቦታዎችን አዳረሰ:: በቅድስናው ወደውታልና የቁስጥንጥንያ ፓትርያርክ አድርገው ሾሙት:: አፈ ወርቅ ሲናገርም ሆነ ሲያስተምር እንኩዋን የሚያወራ ኮሽ የሚል የለም:: ከጣዕመ ትምሕርቱ የተነሳ ሕዝቡ በተደሞ ይሰሙት ነበር:: ሲያስተምር ምድራዊው ሰው ይቅርና ልዑላኑ መላእክት ተሰብስበው ያደንቁት ነበር:: አንዴም እመቤታችን በሕዝብ መካከል "አፈ ወርቅ" ብላ ጠርታዋለች:: ለዛም ነው "አፈ ወርቅ" የሚባለው:: ቅዱሱ በሥልጣነ ቃሉ መልዐከ ሞትን ገስፆ 10 ዓመት አቁሞታል::

+ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ለሰው ፊት አያደላም:: በርሱ ዘንድ ንጉሥና ደሃ ነዳይ እኩል ነው:: ለሞት ያበቃውም ይሔው ነበር:: ምክንያቱም የወቅቱ ንግስት አውዶክስያ ያንዲት ድሃ መበለትን መሬት ቀምታ "አልመልስም" በማለቷ መክሮ አወገዛት:: እርሷ ግን ከኃጥአንና መናፍቃን ጋር መክራ 2 ጊዜ አጋዘችው:: በተሰደደበት ሃገር ፍሬ አፍርቶ: አስተምሮና አሳምኖ በ407 ዓ/ም አርፏል:: ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን ሳይጠግቡት እንደናፈቁት በ60 ዓመቱ አጡት:: በወቅቱ ታላቅ ሐዘንና ለቅሶ ተደረገ::

=>ከዕረፍቱ አስቀድሞ አንድ ቀን የዘመኑ ደግ ንጉሥ አርቃድዮስ ግብር አገባ:: (ግብዣ አዘጋጀ)

በዚያች ሌሊት ደግሞ ቅዱሱ ሊቅ ታጥቆ ሲጸልይ ሳለ: አባ ማርዳሪ የሚባል ጻድቅ ደግሞ ከሰማይ 12ቱ ሊቃነ መላእክት (እነ ቅዱስ ሚካኤል) ከሰማይ በግርማ ሲወርዱ ተመለከተ::

+ደንግጦ "ወዴት ናችሁ ጌቶቼ" ቢላቸው "ቁስጥንጥንያ: ወደ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንሔዳለን:: እርሱ እመቤታችንን እንደሚያመሰግናት ጌታ ነግሮናልና" አሉት:: "እባካችሁ እኔም የአፈ ወርቅ ምስጋናው እንገለጥልኝ መርቁኝ" አላቸው:: ሊቃነ መላእክቱም መርቀውት ጐዳናቸውን ቀጠሉ::

+በማግስቱ በቤተ መንግስት ውስጥ ሊቃውንቱ: መሳፍንቱ: ዻዻሳቱ: ሕዝቡ ሁሉ ተሰብስበው ከድግሱ በሉ:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ግን በመንበሩ ተቀምጦ ነበር እንጂ አልበላም:: ድግሱ ሲጠናቀቅ ንጉሡ አርቃድዮስ ሊቁን "ጥያቄ አለኝ" ብሎ በጉባኤ መካከል ጠየቀው::

+"ምነው ወንጌላዊ ማቴዎስ 'ኢያዕመራ ዮሴፍ እስከ አመ ወለደት ወለደ ዘበኩራ-የበኩር ልጇን እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም' ማለቱ (ማቴ. 1:25) ስለ ምን ነው?" ቢለው ቅዱሱ ተነስቶ: በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ይተረጉምለት ጀመር::

+"ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን ትመስላለች:: ብርሌ የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ ይቀያየራል:: እመቤታችንም ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ መለኮቱ ሲለዋወጥ መልኩዋ አብሮ ሲለዋወጥ እያየ ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር::

+'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ ያለውስ ማን ነው?' እያለ ይጨነቅ ነበር:: ጌታን ከወለደች በሁዋላ ግን አንድ ሕብረ መልክ ሆናለችና:: አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች አላወቀም::

+አሁን ግን ልጇ አምላክ ዘበአማን: እርሷም ወላዲተ አምላክ መሆኗን አወቀ ማለት ነው" እያለ ሲተረጉም ሰምተው ሁሉም ሲያደንቁ በዚያ የነበረች ስዕለ አድኅኖ "አፈ ወርቅ! ልሳነ ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች::

+ያን ጊዜ አርቃድዮስ የወርቅ ልሳን በሊቁና በስዕሏ ላይ አደረገ:: አፈ ወርቅ ግን ባጭር ታጥቆ "እሰግድ ለኪ! እሰግድ ለኪ! ወእዌድሰኪ . . ." ብሎ ዛሬ በተአምረ ማርያም የምናውቀውን ምስጋና ሰተት አድርጐ አደረሰላት:: ይህንን ምስጋናም ሊቃነ መላእክቱ ሰምተው እያደነቁ ወደ ሰማይ ወጥተዋል::

=>ቅዱሱ ሲጠራ እንዲሕ ነው:-
¤ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
¤አፈ በረከት
¤አፈ መዐር (ማር)
¤አፈ ሶከር (ስኩዋር)
¤አፈ አፈው (ሽቱ)
¤ልሳነ ወርቅ
¤የዓለም ሁሉ መምሕር
¤ርዕሰ ሊቃውንት
¤ዓምደ ብርሃን (የብርሃን ምሰሶ)
¤ሐዲስ ዳንኤል
¤ሊቀ ዻዻሳት ዘበርትዕ (እውነተኛው)
¤መምሕር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ
¤ጥዑመ ቃል - - -

አባ ዘካርያስ ገዳማዊ

=>ይህ ታላቅ ጻድቅ ባለ ጥዑም ዜና ነው:: ወላጆቹ እሱንና አንዲት ሴትን ከወለዱ በሁዋላ አባቱ መንኖ ገዳም ገባ:: ከዘመናት በሁዋላ ረሃብ በሃገሩ ሲገባ እናቱ ወስዳ ለአባቱ ሰጠችው:: ይህን ጊዜ ዕድሜው 7 ዓመት ነበር::

+በገዳም ከአባቱ ጋር ሲኖር ከመልኩ ማማር የተነሳ አባቶች መነኮሳት "ይህ ልጅ ይህን መልክ ይዞ እንዴት መናኝ መሆን ይችላል!" ሲሉ ሰማ:: በሌሊትም ተነስቶ በሕጻን አንደበቱ "ጌታየ! መልኬ ካንተ ፍቅር ከሚለየኝ መልኬን አጠፋዋለሁ" አለ:: ከገዳሙም ጠፋ::

+አባትም በጣም አዘነ:: ከ40 ቀናት በሁዋላ ግን ሊያዩት የሚያሰቅቅ: አካሉ ሁሉ የቆሳሰለ አንድ ነዳይ ሕጻን መጥቶ ወደ ገዳሙ ተጠጋ:: ይህ ሕጻን በጾም: በጸሎትና በትሕትና ተጠምዶ ለ45 ዓመታት አገለገለ::

@degnitKindness

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

22 Oct, 06:59


እጅግ ድንቅ ትምህርት!!


ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ


በማስተዋል እናዳምጥ ሰናይ ቀን


💖

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

22 Oct, 03:18


ቅዱስ ሚካኤል

ቅዱስ ሚካኤል ወዳጅ ነህ ለሁሉ
ዛሬም ቆመሀል በኪዳንህ ላሉ
አዝ።።።።።
ክንፍህን ዘርጋ ሚካኤል ቅደም ከፊቴ
ምራኝ መንገዱን እንዳይመሽ ልድረስ ከአባቴ
እንዴት ይገፋል ጎዳናው ያላንተ እርዳታ
ጥሜን ቁረጠው በትርህ ጭንጫውን ምታ
አዝ።።።።
ተጠመጠመ ጠላቴ በእሳት ሰንሰለት
የጌታ መልአክ ሚካኤል በሰይፍ ወድቆበት
የለም በቦታው ስመለስ አጥቼዋለሁ
የሚረዳኝን ተሹሞ አይቼዋለሁ
አዝ።።።።
ከመቃብሩ ድንጋዩን አንከባለሃል
ስለረዳኸው ዳንኤል እጅግ ወዶሃል
ይነዋወጻል ባሕሩም አንተ ስትመጣ
እግዚአብሔር ይንገስ ዲያብሎስ መድረሻ ይጣ
አዝ።።።።።።
አለኝ ትዝታ በቤትህ ከልጅነቴ
ስትሳሳልኝ እያየሁ ፀንቷል ጉልበቴ
ልዘምር እንጂ ላመስግን ታላቁን ጌታ
አንተን የሰጠኝ ጠባቂ በቀን በማታ

ዘማሪት ምርትነሽ ጥላሁን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

22 Oct, 03:18


ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አደራችሁ እህት ወንድሞች


እንኳን ለሊቀ መላእኩ ቅዱስ ሚካኤል ወርኃዊ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን

ቅዱስ ሚካኤል ከክፉ ሁሉ ይጠብቃችሁ ..

=======🤲

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

21 Oct, 20:26


✝️ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞


❖ ጥቅምት ፲፪ (12) ❖


✞ እንኳን ለልበ አምላክ "ቅዱስ ዳዊት":
ለቅዱስ "ማቴዎስ ሐዋርያ" እና ለቅዱስ "ድሜጥሮስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞



ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ

=>ቅዱስ መጽሐፍ እንዲህ ይላል:- "እግዚአብሔር ለዳዊት በእውነት ማለ: አይጸጸትም::" (መዝ. 131:11) አሁን በእግዚአብሔር መጸጸት ኑሮበት አይደለም:: ቅዱስ ዳዊት የማያጸጽት ፍጹም ወዳጅ መሆኑን ሲገልጥ ነው እንጂ:: ጌታ ቅዱስ ዳዊትን "እንደ ልቤ የሆነ: ፈቃዴን የሚፈጽም: ባሪያየን ዳዊትን አገኘሁት" (መዝ. 88:19) ብሎ ሲናገር ሰምተን እጅግ አደነቅን::

+እንደ አምላክ ልብ ሆኖ መገኘት ምን ይረቅ?! ምንስ ይደንቅ?! ለዚህ አንክሮ ይገባል !! ጌታ ይቀጥልና ደግሞ "ዳዊትን እንዳልዋሸው አንድ ጊዜ በቅዱስነቴ ማልሁ" (መዝ. 88:35) ይላል:: *" አቤት አባታችን ዳዊት!!! . . .ክብር: የክብር ክብር: ውዳሴና ስግደትም ላንተ በጸጋ ይገባል "* እንላለን::

✞ ነቢየ ጽድቅ ቅዱስ ዳዊት 7 ሃብታት ሲኖሩት:-
1.ሃብተ ትንቢት
2.ሃብተ መንግስት
3.ሃብተ ክህነት
4.ሃብተ በገና (መዝሙር)
5.ሃብተ ፈውስ
6.ሃብተ መዊዕ (ድል መንሳት)
7.ሃብተ ኃይል ተብለው ይታወቃሉ::

በ7ቱ ስሞቹም:-
1.ጻድቅ
2.የዋህ
3.ንጹሕ
4.ብእሴ እግዚአብሔር
5.ነቢየ ጽድቅ
6.መዘምር እና
7.ልበ አምላክ ተብሎ ይጠራል::

† ይህች ቀን ለእሥራኤል የነገሠባት ቀን ናት:: እግዚአብሔር ሳዖልን ከናቀው በሁዋላ ከእሴይ ልጆች መካከል "እንደ ልቤ የሆነውን ቀብተህ አንግስልኝ" ቢለው በዚህች ቀን ነቢዩ ሳሙኤል ቤተ ልሔም ገብቷል::

+በዚያም ከኤልያብ እስከ አሚናዳብ: 7ቱን የእሴይን ልጆች ቢፈትን አልሆነም:: በቅዱስ ሚካኤል ጠቁዋሚነት ግን ከእረኝነቱ ዳዊት ተጠራ:: ገና ከርቀት ሲመጣ የዘይት ቀርኑ ቦግ ብሎ ተከፈተ::

+በቅዱስ ዳዊት ራስ ላይም እንደ እሳት ፈላ:: በአምላክ ምርጫም በ12 ዓመቱ ንጉሥ ተባለ:: የቅዱሱ ዜና ብዙ ነውና ለታሕሳስ 23 ይቆየን:: በቸር ቢያደርሰን በዚያው ቀን ከክብሩ እንካፈላለንና::

ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ


=>ቅዱሱ በቀዳሚ ስሙ "ሌዊ": በቀዳሚ ግብሩ ደግሞ "ቀራጩ" ይባል ነበር:: ወንጌል እንደሚል ጌታችን የጠራው ከሚቀርጥበት ቦታ ሲሆን (ማቴ. 9:9) ከ12ቱ ሐዋርያት ደምሮ (ማቴ. 10:1) ስሙን "ማቴዎስ" ብሎታል:: ትርጉሙም "ኅሩይ" (ምርጥ) እንደ ማለት ነው::

+ጌታችንን በዘመነ ሥጋዌው በፍጹም ምናኔ ከማገልገሉ ባለፈ ከዋለበት እየዋለ: ካደረበት እያደረ: የእጁን ተአምራት ተመልክቷል:: የቃሉንም ትምሕርት ሰምቷል:: በጌታ ሕማማት ጊዜ ምንም በፍርሃት ከተበተኑት አንዱ እሱ ቢሆን አመሻሽ ላይ ወደ ማርቆስ እናት ቤት (ጽርሐ ጽዮን) ሒዶ ወንድሞቹን ሐዋርያትን ተቀላቅሏል::

+የክብር ባለቤት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተነስቶ ትንሳኤውን ሲገልጥም ቅዱስ ማቴዎስ ነበረ:: ለ40 ቀናት መጽሐፈ ኪዳንን: ትምሕርተ ኅቡዓትን ተምሮ በጌታ ዕርገት ጊዜ ሊቀ ዽዽስናን ተሹሟል:: በ50ኛው ቀን መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜም ጸጋውንና 71 ልሳናትን ተቀብሎ በኢየሩሳሌምና በዙሪያዋ ወንጌልን ሰብኩዋል::

+ሐዋርያት ወንጌልን ለዓለም ለማዳረስ እጣ በተጣጣሉ ጊዜ ለቅዱስ ማቴዎስ ምድረ ፍልስጥኤም ደረሰችው:: ሃገረ ስብከቱን ካዳረሰ በሁዋላም ወደ ሌሎች ሃገራት ተጉዞ ሰብኩዋል::

+ለምሳሌ በገድለ ሐዋርያት ላይ በኢትዮዽያ: በፋርስና በባቢሎን አካባቢ ማስተማሩን ይገልጻል:: የሚገርመው ደግሞ ለዚህ ማረጋገጫ የሚሆን ነገር ሃገራችን ውስጥ መኖሩ ነው::

+ወደ አክሱምና አካባቢዋ ቅዱሳት መካናትን ለመሳለም በሔድንበት ወቅት በጻድቃነ ዴጌ/ዶጌ ገዳም ውስጥ (አክሱም አካባቢ የሚገኝ የ3ሺ ስውራን ቦታ ነው) የቅዱስ ማቴዎስን በትረ መስቀል መመልከት ችለናል:: አባቶችም ቅዱስ ማቴዎስ በዘመነ ስብከቱ አክሱም አካባቢ መጥቶ እንደ ነበር ነግረውናል::

+ቅዱሱ ሐዋርያ በአይሁድ: በአሕዛብና በአረሚ መካከል እየተመላለሰ አስተምሮ በርካታ ተአምራትን ሠርቷል:: የጣዖት ካህናትንና ነገሥታትን ጨምሮ እልፍ አእላፍ ነፍሳትን ወደ ክርስትና መልሷል::

+ስለዚህ ፈንታም እጅግ ብዙ መከራዎች ተፈራርቀውበታል:: ጌታችንም በየጊዜው እየተገለጸ ያጽናናው ነበር:: በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያውን ወንጌል በምድረ ፍልስጥኤም ሲጽፍ: ዘመኑም ጌታ ባረገ በ8ኛው ዓመት (ማለት በ43 ዓ/ም) አካባቢ ነው::

+ወንጌሉ 28 ምዕራፎች ሲኖሩት በጌታ የዘር ሐረግ ጀምሮ የጌታችንን ትምሕርቱንና ተአምራቱን በሰፊው ያትታል:: በመጨረሻም ከምሴተ ሐሙስ እስከ ትንሳኤ ድረስ አትቶ ይጠናቀቃል::

+ቅዱስ ማቴዎስ ከ12ቱ ሐዋርያት በአንድ ነገሩ ይለያል:: ከ5ቱ ዓለማት አንዱን (ብሔረ ብጹዓንን) ያስተምር ዘንድ ተመርጧል:: ዘወትር እሑድ በደመና እየተነጠቀ ኃጢአት ወደ ሌለበት ዓለም ገብቶ ብጹዓንን ያስተምር ነበር:: "ሰላም ለማቴዎስ በደመና ሰማይ ዘተነጥቀ: ኅሩያነ ይርዓይ ዘብሔረ ብጹዓን ደቂቀ::" እንዲል::

+በዚያም ዘወትር ጌታችንን ያየው ነበር:: ቅዱስ ማቴዎስ እንዲህ ከተመላለሰ በሁዋላ በፍጻሜው ለጊዜው ባልለየናት አንዲት ሃገር ውስጥ አረማውያን አስረው አሰቃይተውታል:: በዚህች ቀንም ገድለውታል::

ቅዱስ ድሜጥሮስ

=>ቅዱስ ድሜጥሮስ በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን የተወለደ: በመንፈሳዊ ለዛ ከአጐቱ ደማስቆስ ጋር ያደገ የዘመኑ ደግ ሰው ነበር:: በዘመኑ ክርስቲያኖች በሰማዕትነት ያለቁበት በመሆኑ ቤተሰቦቹ የአጎቱን ልጅ ልዕልተ ወይንን እንዲያገባ ግድ አሉት::

+ቅዱስ ድሜጥሮስ የነርሱን ፈቃድ ለመፈፀም ጋብቻውን በተክሊል ፈፀመ:: የፈጣሪውን ፈቃድ ለመፈፀም ደግሞ ከቅድስት እናታችን ልዕልተ ወይን ጋር ተስማምተው ለ48 ዓመታት በአንድ አልጋ ላይ እየተኙ: አንድ ምንጣፍና ልብስ እየተጋሩ በድንግልና ኑረዋል:: ቅዱስ ሚካኤልም ስለ ክብራቸው ከመካከላቸው ሆኖ ቀኝ ክንፉን ለርሱ: ግራ ክንፉን ለርሱዋ ያለብሳቸው ነበር::

+ከ48 ዓመታት በሁዋላ ቅ. ድሜጥሮስ የግብፅ 12ኛ ሊቀ ዻዻስ ሆኖ ተሹሞ ምስጢር በዝቶለት ባሕረ- ሐሳብን ጽፎ ሠርቷል:: ሰይጣን በሰዎች አድሮ ቅዱሱን ሚስት አለው በሚል ቤተ ክርስቲያን ላይ ሁከት በመፈጠሩ ቅዱስ ድሜጥሮስ በመልዐኩ ትእዛዝ ሕዝቡን ሰብስቦ: እሳት አስነድዶ: ከቅድስት ልዕልተ ወይን ጋር እሳቱ ውስጥ ገብተው ለረዥም ሰዓት ጸልየዋል::

+ሕዝቡም ይሕን ተአምር አይተው: የቅዱሳኑን ንጽሕና ተረድተው: ማረን ብለው በፍቅር ተለያዩ:: መጋቢት 12 ቀን ድንግልናው ተገልጧል::

+ቅዱስ ድሜጥሮስና እናታችን ልዕልተ ወይን ተረፈ ዘመናቸውን በቅድስና አሳልፈዋል:: በተለይ ሊቀ ዻዻሳቱ ድሜጥሮስ ብዙ ድርሳናትን ደርሷል:: እነ አርጌንስ (Origen) ና ቀሌምንጦስ ዘእስክንድርያ (Clement of Alexandria) የመሰሉ መናፍቃንንም አውግዟል::

+ከጣዕመ ስብከቱም የተነሳ አርጅቶ እንኩዋ ምዕመናን እየተበሰቡ ይማሩ ነበር:: በአልጋ ተሸክመውም ይባርካቸው ነበር:: ቅዱሱ በ107 ዓመቱ ያረፈው በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን አጋማሽ አካባቢ በዚህች ቀን ነው::

=>አምላከ ዳዊት ፍቅሩን: አምላከ ማቴዎስ
አገልግሎቱን: አምላከ ድሜጥሮስ ንጽሕናውን
ያሳድርብን:: ጸጋ በረከታቸውን ደግሞ ያትረፍርፍልን::

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

21 Oct, 20:26


† ጥቅምት 12 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን
በዓላት


1.ቅዱስ ዳዊት ልበ አምላክ (የነገሠበት)
2.ቅዱስ ማቴዎስ ሐዋርያ
3.ቅዱስ ድሜጥሮስ ሊቅ
4.ቅድስት ልዕልተ ወይን
5.ቅዱስ ሳሙኤል ነቢይ
6.ጻድቃን ዼጥሮስ ወዻውሎስ


† ወርሐዊ በዓላት

1.ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት
2.ቅዱስ ላሊበላ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
3.ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
4.ቅዱስ ቴዎድሮስ ምሥራቃዊ (ሰማዕት)
5.ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
6.አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ

=>"ከሕዝቤም የተመረጠውን ከፍ ከፍ አደረግሁ::
ባሪያየን ዳዊትን አገኘሁት:: ቅዱስ ዘይትም ቀባሁት:: እጄም ትረዳዋለች:: ክንዴም ታጸናዋለች:: ጠላት በእርሱ ላይ አይጠቀምም:: የዓመጻ ልጅም መከራ አይጨምርበትም:: ጠላቶቹን ከፊቱ አጠፋለሁ:: የሚጠሉትንም አዋርዳቸዋለሁ:: "(መዝ. 88:20)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት - ዘብሔረ ጎንደር [ዲ/ዮርዳኖስ አበበ]

@degnitKindness

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

21 Oct, 08:46


አትጨነቁ


መ/ር እዮብ ይመኑ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

21 Oct, 03:41


ከመ ጽጌ ሮማን ከመ ጽጌ
አበባዬ /2/ ወላዲተ አምላክ ሲሳዬ

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

21 Oct, 03:41


ምዕረ በዘባንኪ ወምእረ በገቦኪ
በሀዚለ ሕጻን/4/ ደከምኪ ማርያም ብዙኃን

ደግነት በጎ አድራጎት ማኅበር

21 Oct, 03:41


🙏ተራ ድብቅ (ልታይ የማትል) ዝምተኛና ታናሽ ሰው ሁን

🙏ወደራስህ ትኩረትን ፈፅሞ አትሳብ

🙏ሰዎች ሲያናግሩህ አድምጣቸው

🙏ነገሮችን በንቃት ተከታተል

🙏ከሚያስፈልጉህ ውጪ አትናገርም አትስብም

🙏ስታወራ በግልፅ በአፅንኦት እና በቀላሉ አውራ

🙏ነገሮችን ከማለም ከማሰላሰል እና ከምኞት ራቅ


#ብሂለአበዉ የህይወት መመሪያዎች


እንደምን አደራችሁ ቤተሰብ❤️

27,019

subscribers

2,519

photos

98

videos