ሐሽማል ቤተ-መዘክር @amharicbooksforeaders Channel on Telegram

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

@amharicbooksforeaders


👉Only for readers
👋መግቢያ👋

መግቢያ ለመግባቢያ
ገታ አርገነዋል የቃላትን ግልቢያ
እናም በዚህ ሀሳብ ከተስማማህበት
ያንኳኳኸዉን በር የገለፅከዉን ገፅ ፈቅደናል ግባበት

ምንጭ - ካልታወቀ ገጣሚ
Join the group
@amharicbooksforeadersgroup
አድሚኑን በ ቀጥታ ለማናገር ይህንን ቦት ተጠቀሙ @Digitallibraryofhashmal_bot

ሐሽማል ቤተ-መዘክር (Amharic)

የሀሽማል ቤተ-መዘክር ጨምሮ ከሃሳብ ገታ አርገነዋል የቃላትን ግልቢያ በመምላም እና በስነ-ስርዓት ከባለዉን ገጽ እና ውጤቶችን ግባበታዊ ተጠቃሚዎችን እናም በር የገለፁን ሳይበረታት ውጤትን በሚሰማበት መጽሀፍ በማግኘት ከባለዉን የሃሳብን ቤተ-መዘክር መዘክርን ልኬቶ በሚከፍትበት እርምጃ እናም ቀጣይ እንቅስቃሴ ይኖርባቸዋል ፦፦ @amharicbooksforeadersgroup ላይ በገጽ ያደርጉበታል። አድሚኑን በ ቀጥታ ለማናገር ይህንን ቦት ተጠቀሙ @Digitallibraryofhashmal_bot ላይ በማግኘት ካሉት ያስራዳል። እባኮትም ባሳምና በየሳተ እንቅስቃሴ እሚሆን በማየት ቤተ-መዘክርን እዚህ በመቅረብ ይጠቀሙ።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

21 Feb, 17:05


ትዕቢተኛ ሴት አልወድም ፤ ንቀት የሚዘውራት ፤ አፈር እንደሆነች የዘነጋች ፥ አፈር አይንካኝ የምትል አይነት...ነገሩ ትዕቢት በሁለቱም ፆታ ያስጠላል።


ከሆነ ጊዜ በኋላ እኮ ምንም ነን ፥ ምድር አታስታውሰንም ፤ ከበታቿ ቀብራ በተረኛ ታስረግጠናለች ።


በተቻለን መጠን ባለቺን ጥቂት እድሜ የሌላውን ሰው ደስታ ሳንነጥቅ ብናልፋትስ ?



ከ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

19 Feb, 20:12


Credit to -የተቀደደው ማስታወሻ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

17 Feb, 11:55


And once the storm is over, you won't remember how you made it through, how you managed to survive. You won't even be sure, whether the storm is really over. But one thing is certain. When you come out of the storm, you won't be the same person who walked in. That's what this storm's all about.


-Haruki Murakami

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

16 Feb, 19:31


ፈላስፋው : ማገዶ ነን እኮ

መንገደኛው ፡ እንዴ እንዴት ፈላስፋው ?

ፈላስፋው ፡ እኛ እየነደድን የሌላውን ቤት የምናሞቅ የሞቀን እየመሰለን እየነደድን ያለን ክቡር ማገዶዎች ..

መንገደኛው ፡ አልገባኝም

ፈላስፋው ፡ ሳይህ ሰሚ ትመስላለህ ግን ለሀሜት ሳይሆን ለህይወት ስማ

አልገባኝም ላልከው ደሞ አንድ ምሳሌ ልስጥህ አንተ ከፍተህ በምትጠቀመው የ Facebook አካውንት የMark Zuckerberg ቤት እና ኑሮ ያድጋል የአንተ ደሞዝ እና ቤት ደሞ ይናጋል መቼም የማገዶ ባህሪ መንደድ አይደል ?

✍️ ሔኖክ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

16 Feb, 17:20


ድፍረት ማለት ያለ ፍርሀት መኖርና እየደነፉ ማውራት ማለት ሳይሆን ፣ከሚገባው በላይ ብንፈራና ብንደነግጥም እንኳን ያሰብነውን ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ አለማለት ነው ።

በአስቸጋሪ ጊዜና ሁኔታ ውስጥ ተረጋግቶ መውጫ ቀዳዳ በመሻት  መውጣት የድፍረት አንድ አካል ነው

ድፍረት ማለት የፍርሀት አለመኖር ሳይሆን ፍርሀት ላይ የምንቀዳጀው ድል እንደሆነ ተማርኩ፤ ጀግና የሚባለው ፍርሀት የማይሰማው ሳይሆን ፍርሀትን መማረክ የቻለው ነው!

----ኔልሰን ማንዴላ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

15 Feb, 19:58


ተይው
(kerim)


ተይው አላገግም
መዳን አልፍልግም

ስለ አንቺ መታመም መዳኔ ነው እና
አንቺን በማፍቀር ውስጥ እኔ ልጣ ጤና
ተይው........

By @poem2513

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

14 Feb, 08:56


በህይወታችን ከሶስት ሰዎች ጋር በፍቅር እንወድቃለን: ሶስቱም የራሳቸው ምክንያት አላቸው ይላሉ

👇🏾

የመጀመርያው ፍቅር በአፍላ እድሜ ወቅት የሚከሰት ነው: ድንገት መጥቶ እፍ ያስብልና ከዚያም እዚህ ግባ በማይባል ምክንያት መራራቅ ይፈጠራል

ከቆይታ በኃላ በእድሜ ስንበስል መለስ ብለን ስናየው ፍቅር እንደነበር ራሱ የምንጠራጠረው አይነት ስሜት ነው: ግን በወቅቱ ፍቅር እንደሆነ ተሰምቶን አልፏል

.............

ሁለተኛው ፍቅር ከባዱ ነው

በፍቅር ከወደቅነው ሰው ጋር እፍ ማለት ብቻ ሳይሆን ብዙ ህመም እና ስብራትም ይዞ የሚመጣ ነው:: እንዲህ አይነት ፍቅር ስሜቱ ሃያል ሲሆን ቁርኝቱ ከመክረሩ የተነሳ ከዚያ ሰው ጋር መለየት የሞት ያህል የከፋ ይመስለናል

ስለዚህ በዚህ ፍቅር የተጎዳነውን ስብራት በምንጠግንበት ሂደት "ከዚህ ወዲያ ልቤን ብሰጥ እርም" ወደሚል አጥር የመስራት ውሳኔ ውስጥ እንገባለን: ጠባሳው ትልቅ ሊሆን ይችላል

ስለዚህ ተጠራጣሪ እንሆናለን: በቀጣይ ፍቅር ሲይዘን እንዴት እንደምንሆን ቀመሩን እንወስናለን: ከስሜታዊነት ፈቀቅ እንላለን

.................

ሶስተኛው ፍቅር መምጫው ሳይታወቅ ድንገት የሚመጣ ነው ይሉታል

ይህንን አይነት ፍቅር ብዙም ለማግኘት ተደክሞ ሳይሆን ድንገት የሚይዘን ነው: ድንገት የገነባነውን ግድግዳ ሁሉ የሚያፈራርስ አይነት ፍቅር ይሉታል

እዚህ ጋር ካፈቀርነው ሰው ጋር የሚኖረን ግንኙነት "ከወደዱማ ከነግሳንግሱ" አይነት ሲሆን አንዱ ሌላውን እየቀረፀ የተሻለ ማንነት የሚሰራበት ነው

ጠዋት ከእንቅልፍ ስትነሳ "Good Morning my Sunshine” የምትልለት እና ማታ ስትተኛ ደግሞ "Good Night Darling” ብለህ ቀንህን ጀምረህ ቀንህን የምታሳርግበት

እንማር

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

13 Feb, 16:18




ስወድሽ በቅፅበት ነበር ፥ ሳፈቅርሽ ቀን አላለፈም
ቆም ብሎ እንኳን ለማሰብ ፥ በመሀል ጊዜ አልተረፈም ::
አይኖቼ አይንሽን አዩ ፥ የልቤ መቃን ወለቀ
ፈገግታሽ ሙት አፌን ነክቶት ፥ ግማታም ጥርሴ በድንገት ሳቀ።
መዳፍሽ መዳፌን ያዘ፥ ትንሽ ላብ እጄን አራሰው
ያን ጊዜ ሞፈሩ ፍቅርሽ ፥ ደንዳና ልቤን አረሰው ።

አየሻ...

ከአይን ጥቅሻ ቀድሞ ነበር፥ ፍቅርሽ ልቤን ያነቀው
ነገር ግን ዓመት ፈጀበት ፥ የኔ ፍቅር ልብሽን ሊያውቀው
"ወደድኩህ " አልሺኝ ባመቱ
ደስ ብሎኝ ነበር በውነቱ
ግን እቱ.....

ማፍቀርሽ እሩጫ ነበር፥ ከራስሽ ችግሮች ሽሽት
ትዝ ይልሻል የዛን ምሽት ?
[ I Know, You Don' Give A Shit ]
ግን አስታውሺ,....
" የት ነሽ ? " ብየሽ ስትዋሺ....

ማጋጣነት ካቀለመው ፥ ድፍን ጥቁር ልብሽ ግርጌ
ጥለሽ መክዳትሽ ሲረግጠኝ ፥ መሞት ሲያቅተኝ ፈልጌ
የሞት ከንፈር ዳሩን ስሜ ፥ ልክ ስመለስ ወደ ቀለቤ
ጠላሁሽ.......፥ [ በወደደሽ ልቤ ። ]

[ አየሽ አይደል ? ]
ፍትህ ሰፍኖ ሲደላደል ?

በቅፅበት እንዳልወደድኩሽ ፥ በቅፅበት ስጠላሽ ደግሞ
በንክሻ ሲያስወጣሽ ልቤ ፥ እንዳላስገባሽ ስሞ ?

ግን ደግሞ... ግን ደግሞ....
ማታ አፍቅሬሽ ተኝቼ ፥ ጠዋት ጠልቼሽ ብነቃም
( ልፋ ሲለኝ እንጂ...)
ጨርሶ አንቺን ለመርሳት ዘላለም እንኳን አይበቃም።


<<

" Love is so short, forgetting is so long. " _ Pablo Neruda

''You may forget with whom you laughed, but you will never forget with whom you wept." _ Kahlil Gibran

>>

፦ ግዑዝኤል
0 1 / 06/17
ቅዳሜ
ቀን 8:01

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

12 Feb, 18:07


አንዳንዴ ጉረኛ ሰዎች ደስ ይላሉ ። ወርያቸው አካሄዳቸው ላይ Energy አለ ። ጨለማ ..ጨለማ.. ብሶት.. እዬዬ ። አይ ጉድ.. ብዙ ግዜ አያወሩም ።

በራሳቸው ጉዳይ በፍቅር ወድቀዋል ።

ተስፈኛ ናቸው ። ያላቸው ነገር ላይ ይመሰጣሉ ያጎሉታል ።

ምን ለማለት ነው
አንዳንዴ እየጎረርን 😄

እንማር

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

11 Feb, 15:28


የሆነ ቦታ የሆነች የተረጋጋች ሴት ያለች ይመስለኛል። የሰውን ትኩረት የማትፈልግ ፤ ሰዎች እንዲወዷት የተለየ ነገር የማታደርግ የራሷን ኑሮ የምትኖር...

ህይወቷ በእውነት እንጂ በፈጠራ ድራማ ያልተሞላ ፤ ሰዎች እግረመንገድ ላይ ድንገት ዋነኛዋ ሴት የምትሆን ። የተሰማትን የፈለገችውን ደስ ያሰኛትን የምታደርግ ፤ ምታደርገው የማይፀፅታት ...

ምድር ላይ ያለውን የህይወት ብሶቷን አልያም ችግሯን ለመደበቅ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወ'ታ ከመንዘባዘብ ይልቅ ከአምላኳ ጋር የምትነጋገር። ስለራሷ እሷ እና አምላኳ ብቻ የሚያውቁ። ይህቺ ሴት ብርቱ ናት....

ለጓደኝነት ትመቻለች። ነፃነት ትሰጣለች። ለጊዜያዊ የፍቅር ግንኙነት ታስፈራለች። ወንዶች ይጠነቀቁላታል። የትኛውም ወንድ ደፍሮ ሌላዋን ሴት የሚያወራበት መልኩ ይቺን ሴት ሊያወራት አይችልም። ልባም ናት። ለዘላቂ ትዳር የምታስተማምን ሴት። የቤቱ ራስ መሆን የሚችል ፣ ሚስቱ እንድትገዛለት ሆኖ መኖር የሚችል ባል የሆነ ወንድ የሚመኛት እና የሚያገኛት ሴት ናት።

ይህቺ ሴት ብርቅ ናት ! ፀሎቷ ልኬት ያለው ይመስለኛል። ከሚያስፈልጋት በላይ እንዲሰጣት አትለምንም። ተመስገንን ታውቃለች በተሰጣት አታማርርም ።

Via MP ET

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

10 Feb, 10:02


አውቃለሁ!

ባንቺ ዝምታ ውስጥ ነፍሴ ማህሌት ቆማ
ሰማሁ ተመስጬ የልብሽን ዜማ።
አውቃለሁ ዓለሜ ..
ከንፈሮችሽ አፍረው ባይወጣ አንድም ቃል
እንደምትወጂኝ ዓይንሽ ያሳብቃል።

✍️ገጣሚ ዘሪሁን ከ አሰላ
የካቲት 1/2017

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

10 Feb, 00:15


ቻርሊ ቻፕሊን አንድ ቀን ህዝብ ተሰብስቦ ወደሚጠብቀው አዳራሽ አመራ። በጭብጨባ ከተቀበሉት በኋላ ወደ መድረክ እንዲወጣ ተጋበዘ።

#በመጀመርያ የሚያምር ቀልድ ነገራቸው። አዳራሹ በፉጨት ተቀወጠ በሳቅ ደመቀ።

ከዚያም ያንኑ ቀልድ #ለሁለተኛ ጊዜ ደገመላቸው። ግማሾቹ ሳቁ፤ ግማሾቹ ደግሞ ግራ ተጋቡ....

#ለሶስተኛ ጊዜ አሁንም ያንኑ ቀልድ ደገመው። በዚህ ጊዜ ግን አንድም የሚስቅ ሰው አልነበረም።

ያኔ ቻርሊ በጣም ደስ አለው። ከዛም የሚከተለውን ንግግር ተናገረ.....

"በአንድ ቀልድ ደጋግማችሁ እንደማትስቁ ሁሉ ስለምን በአንድ ነገር ደጋግማችሁ ታለቅሳላችሁ?

ህይወትኮ እጅግ ውብ ናት። ዛሬ በህይወት ካላችሁ ነጋችሁን ማስተካከል ትችላላችሁ።

በትላንት ውስጥ ስላጣችሁት ነገር አታስቡ ዛሬን ብቻ በህይወት በመኖራችሁ ፈጣሪን አመስግኑ።

ዛሬ ጠንካራ ከሆናችሁ ነጋችሁ የተዋበ ይሆናል፤ ነጋችሁ የሚጥም ይሆናል። አሁንም አሁንም አሁንም በህይወት መኖራችሁን ብቻ እያያችሁ ፈጣሪን አመስግኑ!"

#ወዳጆቼ ከተሰጠን ስጦታዎች ሁሉ ህይወታችን ይበልጣልና በህይወት ካላችሁ በነጋችሁ ላይ ለውጥ መፍጠር ትችላላችሁ።"
---------------------------
ዳን TELL

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

09 Feb, 09:46


የሠርጌ ቀን እንኳ ብትይ እወድሃለሁ
ሙሽራዬን ትቼ ወዳንቺ እመጣለሁ
ፍቅር ያዘኝ ብልሽ ወደድኩኝ ሌላ ሴት
እየዋሸሁሽ ነው አትስሚኝ በሀሴት
Henok

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

07 Feb, 08:52


ሌላ ሴት ልታገባ ያልክ ቀን እንኳ ብደውልልህ እሷን ትተህ እኔ ጋር ነው አይደል የምትመጣው...? እለዋለሁ ሁሌ ….

ፈገግ ብሎ ያየኝና “ደፋር ኮ ነሽ….ይለኛል።

ካለው ነገር ሁሉ እኔን አስበልጦ እንደሚወደኝ ጠንቅቄ አውቃለሁ...

ሲሳሳልኝ...ከራሱ ሲያስቀድመኝ...ሲጨነቅልኝ...ለኔ ሲኖር ዓይቻለሁ።

....በእርግጥ እንዲህ ማለት ከባድ ይመስላል።

እኔ ግን ዓይኑን ሳያርገበግብ...ይሄን ልጅ ግን ምን አስነክታው ነው እስኪባል... የሚያውቁን ሁሉ እስኪገረሙ ድረስ ሳናድደዉ... እና ሳበሳጨው ችሎ በክፉ ቀናቶቼ ላይ ለደስታዬ ሲፈጋ አብሮነታችንን ለማቆም ብዙ ሲለፋ በህመሜ ወቅት ሃሳቡን ጊዜውን ገንዘቡን ሰጥቶ ከጎኔ ሲቆም አውቅ ነበር....

ይመስለኛል የበዛ መውደዱ.... የትም አይሄድም ብዬ እንዳስብ... ለኛ እንዳልጨነቅ እና በተወዳጅነት ተኮፍሼ ለሚሰጠኝ መውደድ እና ክብር ትንሽ እንኳ አፀፌታን መስጠት የማልችል ሴት አድርጎኛል...

ከዛ በአንዱ ቀን በትንሽ ነገር ተጋጨን እና ….ሂድልኝ አልኩት...

ለመነኝ አስለመነኝ…ከቀልቤ መሆን ያልቻልኩት እኔ ግን ግድ አልሰጠኝም እና ምንም እንደጎደለብኝ አልተሰማኝም።

መሄዱ እንደሚያም እንዴት እንደሚናፍቀኝ ለመረዳት ብዙ ረፈደብኝ...

ሄደ...

ከዛ አልተመለሰም...

ልመልሰዉ ሞከርኩ…መሄድ አለማምጄው ኖሮ መመለስ አቃተኝ...

እናማ አሁን የገፋሁት እኔ....ወዶኛል አይጠላኝም ያልኩት እኔ በተራዬ እጅግ እየናፈቀኝ...እያመመኝ...ነው።

እያስመሰልኩ አብሮነታችን ማክበር ያልቻልኩት እኔ … ሲያቅፈኝ ሕይወት እንደሚቀለኝ ችግሮቼን ችሎ ማሸነፍ ብቻን ያለማመደኝ እሱ እንደነበር...በጣም እንደሚናፍቀኝ...በጣም እንደማመሰግነው እንደምወደው ያልነገርኩት እኔ...

....የሄደበትን ቀን ሻማ እያበራሁ በሐዘን በፀፀት አስታውሰዋለሁ።

(ወግ ብቻ)
(በማ ሂ )

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

06 Feb, 18:10


ዛሬ ላይ የጎዳህ ሁኔታም ይሁን ሰው ፤ ነገም ላይ መጉዳቱ አይቀርም። የባሕርን ጨዋማነት ለማረጋገጥ ባሕሩን ሙሉ መጠጣት አይጠበቅብህም።


የማወራው ስለባሕር አይደለም።
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

02 Feb, 08:58


ህይወት እንደ ማስታወሻ ደብተር ናት።ሁለቱ ገፆች በእግዜር የተፃፉ ናቸዉ።የመጀመሪያው ገፅ የተወለድንበት ቀን ሲሆን ፤የመጨረሻው ገፅ ደግሞ የመሞቻ ቀናችን ነዉ።በመሀል ያሉትን ባዶ ገፆች በፍቅርና በመልካምነት አኛ የምንሞላቸዉ ናቸዉ።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

31 Jan, 19:17


ኮስታራ ናት እንኳን ገና ላልቀረበቺው ቀርቶ ለቀረቧትም ፊቷ አይፈታም።ጭምት ናት።ለሰዎች ደግ እና ቁምነገረኛ መሆኗን ግን ብዙ ሰው ይስማማበታል።እኔ ደግሞ ጥሎብኝ ኮስታራ ሰው እወዳለሁ፤ምንም እንኳን ሳቂታ ብሆንም...ለምንም ነገር ሳቅ ይቀድመኛል...ስናደድ እንኳን እስቃለሁ።
"ያለ ሳቅ ህይወት ምንድነው?" ብዬ የማስብ አይነት ሰው ነኝ።

የእሷ ህይወት?
ሳቅ ፈፅሞ የማይታወቅበት ጨለማ ነው ብዬ ደመደምኩ...የማስፈልጋት መስሎ ተሰማኝ...ለጨለመ ህይወቷ ጭላንጭል ብርሃን ልሆን...ፋኖሴን ይዤ ቀረብኳት፥ፈገግታዬን።
አልገርምም?
ማን ነኝ ብዬ ነው የማስበው?

የመጀመሪያ ሰሞን በቀልድ የተከሸኑትን ረጃጅም አረፍተ ነገሮች...በአጭር መልስ ድባቅ መትታ ጨዋታ ታስጠፋብኝ ነበር።እንኳን ለማሳቅ በወጉ ለማውራትም ቃላት እያጠረኝ መጣ...ይቺ ሴት ፋኖሴን፥ፈገግታዬን እፍ ብላ አጥፍታ እኔንም ያለሳቅ ልታስቀረኝ ነው?

እሷን ሳያት "በፌዘኞች ወንበር አትቀመጥ" የሚለውን የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅስ አስታውሰዋለው...በተገናኘንባቸው አጋጣሚዎች ላስቃት ስውተረተር፣ቃላት ጠፍቶብኝ ስደናበር...ርቃኝ ልደርስባት ስንጠራራ...በቀልዶቼ ሳይሆን በሁኔታዬ ፈገግ ማለት ጀመረች...ኋላ ላይ ሁኔታዬ አሳዝኗት ነው መሠል እሷው ታስቀኝ ጀመር...

አልፎ አልፎ እንደ ቅመም ጣል የምታደርጋቸው ቀልዶቿ ሆዴን አስይዘው ያስቁኛል...በሳቄ እሷ ትስቃለች...ሳቋ ደስ ይለኛል...ሳቋን ለማየት አንዳንዴ እንዲሁ እገለፍጣለሁ።

አንድ ቀን ብዙ ግርግር በማይበዛበት እሷ ባሳየቺኝ ካፌ ቁጭ ብለን ስንጨዋወት..."ከሳቅ ያኳረፈሽ ምንድነው?" ብዬ ጠየኳት።መልሱን ለመስማት ከመጓጓቴ የተነሳ መላ አካላቴ ጆሮ የሆነ እየመሰለኝ።

ጥያቄን በጥያቄ መለሠች። " ሰው ስለሳቀ ደስተኛ ነው ማለት ነው? " አለቺኝ በአይኖቿ ትኩር ብላ እየተመለከተቺኝ።
"ይመስለኛል...ሳቅ የደስታ መገለጫ አይደል፤እንባ ደግሞ የሐዘን።" አልኳት።
"ሐሴት ምን እንሆነ ታውቃለህ?" አለቺኝ።
"ደስታ አይደል"አልኳት በጥርጣሬ።
"አዎ ነው ግን ምን አይነት ደስታ?" ዝም አልኳት ግራ መጋባቴን አይታ ቀጠለች።
"ውስጣዊ ደስታ!" አለችና እርካታ የተሞላበት ፈገግታ ተጎናፀፈች...ሐሴት አደረገች?
ማብራሪያዋን ቀጥላለች "...ሐሴት ማለት ከትክክለኝነት የሚመነጭ ደስታ ነው...አደርገዋለሁ ያልከውን ስታደርገው ነኝ ያልከውን ስትሆን...ብዙዎቹን የራቀው ደስታ ይሄ ነው...እኔ ደስ እንዲለኝ...በየማዕበራዊ ገፁ የሚያሥቅ ነገር ሳስስ ውዬ አላውቅም...ውጪያዊ ደስታ ውሥጥን አርክቶ አያውቅም፤ይልቅ ባዶነት እንዲሠማህ ያደርጋል አንዳንዴም...ሰዎች ደስታ ውስጣቸው እንዳለ ዘንግተውት ደስታን ፍለጋ አይሆኑ ሲሆኑ ያሳዝኑኛል።እኔ ምንም እንኳን ባልስቅም ውስጤ ባለው ሰላም ሐሴት አደርጋለሁ። "

አለች ፍፁም መረጋጋት እና ስክነት ከሁናቴዋ እያነበብኹ።

ከተለያየን ፤ ከሄደች በኋላ ራሴን ጠየቅኹ...

እውነት ደስተኛ ነኝ?
እንጃ!

እኔም ብሎ ፋኖስ ለኳሽ፤ብርሃን አብሪ

እፍፍፍፍፍ....ፋኖሴን(ፈገግታዬን) አጠፋዋት!

ደግሞ ለፀሐይ የፋኖስ ብርሃን ምኗ ነው?
ለካ ጨለማ የነበረው የእኔ ህይወት ነው።




ከተቀደደው ማስታወሻ
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

30 Jan, 23:48


እቴ ወይ ልዋል(2)
ከደረትሽ መሀል
ናፈቀችኝ ጎንደር(2)
የእነ አሞራው ሀገር

በቅዳሴው ቦታ ቀለሀ ሲዘምር
እንዴት ሰንብተሻል እናትዋ ጎንደር
እናትዋ ብልሽ
ትንፋሽዋ ብልሽ
አካልዋ ብልሽ
መቼ ደረስኩልሽ

ሹርባ ሆኗል ጎፈሬው
እንደ መይሳው ሊያደርገው
ያ ጎንደሬው
ምነው ገብርየን ቢያረገኝ
አሞራው ውብነህ ቢያረገኝ
ከፊት እንድገኝ

አሞራው ከአሞራ(4)

ያየም ሰው ይናገር የነበረም ያውጋ
ተጋጥሟል ይባላል አሞራው ከአሞራ
ጎንደር ጀግና ትውለድ ታሳድግ ፀንሳ
እንደአሞራው ውብነህ ስሙ ማይረሳ
ሀገርና እምነቱን ከእራሱ አስበልጦ
ለጠላት ያለቅሳል ውዳሴውን ገልጦ

ጎንደር ጎንደር ደስ ይበልሽ
ደም መላሽ አርበኛው አሞራው መጣልሽ
የሰው ነው የሰው የሰው አመሉ
ማን መጣ ቢሏችሁ ጎንደሬው ነው በሉ

አሞራው ከአሞራ
ኢትዬጵያን ሊያገባት አብጠሊሷን ቀዶ
ልጇ ደረሰላት ሞት ወዶና ፈቅዶ
ወይ አንች እናታለም ወይ አንች መበለት
እንድሜ ብርክ ሲይዘው ልጅ ይሆናል ጎልበት
ወልቃይት ጠገዴ አጅሬ ጃኖራ
ምን አይነት ፍርድ ነው አሞራው ከአሞራ
አሞራው ከአሞራ(3)

ሲሆን መጡ መጡ እንባል ነበረ
እንሂድባቸው ማሸነፍ ካልቀረ
ደሞ ተዚ ተዚህ ተወዲያ ተወዲህ
ጎንደር ከአንች በፊት ያድርገኝ ተንግዲህ
እናትዋ ጎንደር እጅ የዘረጋችው
ዘነበች መሸሻን ወልዳ የሳመችው
ምድር ቀዝቀዝ ሲል ተላይ እያሞቀው
ይኸው ቀብረር ብሎ አሞራው ጠበቀው
አሞራው ጠበቀው

ሀገር እንደዋዛ ናፍቆት እንደዋዛ
የእነ አሞራው ሀገር የመይሳው ካሳ
አዘዞ ድማዛ
የጃንተከል ዋርካው ወደ መሬት ዘሟል
እንኳን ያደገብሽ ያየሽ በአይኑ ታሟል
እናትዋ ጎንደር

ተይ ደሜ(3)
በላ ልበልሀ እንካንጅ ተቀበል
አሞራው ተነሳ ከእንግዲህ ዝም አትበል
የአለም ፀሀይ እታባ ፊትሽ አይቀየር
የተጠማው በልቶ ለብሶ ጠግቦ ቢያድር
ከተኮሰ ማይስት ጀግና ክንደ ብርቱ
ያ የአርበኛው ምንጣፍ ያ ምጅምር ገጡ
የጦሩ መሳፍንት ፈሪሀ እግዜር ያለው
ከጦር መሀል ሲሄድ ይመስላል ክንፍ ያለው
አሞራው ከአሞራ(8)
አሞራ ምት ለምዶ አካሌ ተቆጣ
ልሂድ ወንድነቴን አሳድሸው ልምጣ
ከዳሽን ላይ ፈልቆ ቀድታ የጠጣችው
የነካትን ሁሉ አቃጥላ ፈጀችው
ከሱዳን ገዳሪፍ ተስቦ እንደ ሰርዶ
ኢትዬጵያን ሰቀላት ያን ሰንደቅ አውርዶ
የአበቅየለሽ ልጆች ዳር እስከዳር ኩሩ
ጎንደር ጀግና አታጣም አትጠራጠሩ(3)
አሞራው ከአሞራ (2)

አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ |

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

30 Jan, 23:47


አሞራው ካሞራ | አስቻለው ፈጠነ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

29 Jan, 14:00


ኔግሮ የሚባል ፍሬንድ ነበረኝ ፀባይኛ ነው፣ ሌባ ነው፥ እናቱን ይወዳታል፥ ትምህርት አይገባውም፤ ተንኮል፣ ኳስ ፣ጆተኒ ፣ ትረባ ጎበዝ ነበር።

በአንድ ሴሚስተር መቶ እና ሁለት መቶ መፅሃፍ ይሰርቃል መቼ? ...እንዴት?...ከማን?... አላውቅም!

መጨረሻ ላይ  ውጤቱን እየሳቀ ይነግረኛል።
አንድ ቀን እንኳን ሲሰርቅ ተይዞ አያውቅም !

የሰረቀውን መፅሐፍ ሲሸጥ አብሬው ሄጄ አውቃለሁ። ከሚገዙት ጋር ደምበኛ እንደሆነ ሰላምታ አለዋወጣቸው ያስታውቃል። አሻሻጡ የሰረቀ ፣ ሳይለፋበት ያመጣ አይመስልም፤ በቸልታ አይደለም።  በርጋታ እንደትልቅ ሰው... "አይሆንም...፣ ይቅር...፣በቃ፣ ጨምር " እያለ ነው ።

እናቱን  "ሸቅዬ... እዛ ማዶ ያሉት ሃብታም ሰዎች፤ ለእናትህ ስጣት ብለው ብር ሰጡኝ" እያለ እንደሚሰጣት ነገሮኝ ያውቃል ።

ሰባተኛ ክፍል ፣ ስምንተኛ ክፍል እያለን እናቱን ያግዛት ነበር ።  ይወዳታል፤  አወዳደዱ እንደትልቅ ሰው  ነው። "ማሚዋ  ደብሯታል ...አሟታል. . . ገበያ ቀዝቅዞባታል" እያለ ያስብላታል።

ከጓደኛው አይሰርቅም። ለጓደኛው ለኔ ለሚለው ሰው ይሳሳል።

አይኖቹ ትናንሽ ናቸው፣ አካባቢውን በትኩረት ያያል፣ ከወሬ ሁኔታን ያያል። ሌባ መሆኑን ብዙ የሩቅ ሰዎች አያውቁም።

ኔግሮ ቁርንጫጭ ፀጉር ያለው፣ ድቅቅ ያለ ገላ ያለው፣ ሲስቅ ቀጭን ድምፅ የሚያወጣ ልጅ ነበር ።

አንዳንድ  ቀን  ይፎርፍና ሜዳ ጥግ ውኃ ልኩ ጋር ብቻውን ይሆናል ። ዝም ይላል ኳስ አይጫወትም። ቀጭን ድምፅ እያወጣ የሚስቃት ሳቅ አትኖርም። ለመኮረጅ ብዙ አይሰቃይም።

...ጨዋታ ያበዛል...።

ስለ አባቱ አላውቅም፤ እናቱ ግን ትምህርት ቤታችን በር ጎን ላይ ቃርያ ፣ ቲማቲም፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ድምብላል፣ ኮሰረት፣ ስኳር ድንች ...ምናምን ይሸጣሉ። ብዙ ደንበኛ ያላቸው አይመስለኝም። ስንወጣ ስንገባ የደራ ገበያ አንድም ቀን አይቼ አላውቅም ።  

ኔግሮ የትምርት ቤት ስሙ መቆያ ነው። እኛ ነን ኔግሮ የምንለው።

እኛ ትምህርት ቤት የሚማሩ የሰፈሩ ልጆች ሲጠሩት ሰምተን መሰለኝ መቆያን ትተን ኔግሮ የምንለው።

መቆያ የሚባለው ክላስ ስም ሲጠራ ብቻ ነው። ኔግሮ ሲባል ነው እሱም ደስ የሚለው።

የሆነ ቀን ሃይሚ ግርማ መፅሃፍ ጠፍቶብኝ ኔግሮ ሰጠኝ አለችኝ። ጠየኩት "ከራሷ ቦክመህ ለራሷ ገጫሃት ኣ?" ስለው ፤ ሲስቅ የሚያወጣትን ቀጭን ድምፅ አውጥቶ ሳቀ  "ባክህ እኔ እንደኔ ችስታ እናት ካለው ቤተሰብ አልሰርቅም "አለ ።

ከስምንት ወደ ዘጠኝ ስንዘዋወር ኔግሮ ታስሯል አሉን። ስሰማ "ዕድሜው ለእስር ደርሷል ወይ?" ብዬ ያኔ አልጠየኩም።

የመንግስት ትምህርት ቤት ስለተማርን ለብዙ ነገር  ከዕድሜያችን በላይ ነበርን። የሚታሰሩት በግሩፕ የሚጣሉ ልጆች ስለነበሩ ብዙ  አልገረመኝም።

መስከረም አስራ ሰባት ቀን ኔግሮ ሞተ አሉን።  እናቱን ስናያቸው ጥቁር ለብሰዋል፥ ጉስቁልናው ብሶባቸዋል። ጉሊት የደረደሩት ከዚህ ቀደም ለመሸጥ ከሚደረድሩት በዐይነትም በመጠንም ቀንሶ አየሁ ።

ሞትን ያኔ ነበር በቅርብ ያወኩት ....በቅርብ የማውቀው፣ ሲያወራ የሰማሁት፣ አብሬው የተጫወትኩት ጓደኛዬ ሞተ ሲባል። ያኔ ነው ለመጀመሪያ ግዜ ያመንኩት።

የታሰሩበት ክፍል የነበረው ካቦ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ፖሊስ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ታሞ ነው ይላሉ ....
ኔግሮ ሞተ። እውነት  ነበር!

"ልጅ ይሞታል እንዴ?!" አልኩኝ
ለምን መቆያ አሉት ግን  እናቱ??
በዛ ዕድሜው እንዴት በዛ ልክ አሰበላቸው??
በምን ይሆን የሚፅናኑት??
ለምን ሌባ ሆኖ ለጓደኞቹ ታመነ??

እንዴት  የሰረቀውን እንደትልቅ ሰው አስቦ ተከራክሮ ሸጠ?? ላለፋበት ነገር እንዴት ዋጋ ሰጠ?? ለምን ምንም ከሌላቸው ሰዎች አልሰርቅም አለ??

በዛ ዕድሜው እንዴት አረጀ ?
እሺ ይሁን መርህ እና ሌብነት እንዴት አብሮ ሄደለት!!

እኔንጃ ኔግሮ ግን ሞተ አሉ !!!
      © Adhanom Mitiku

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

28 Jan, 10:19


እድሜህ ምን አስተማረህ ...??

ሁላችንም ባልተመረመርናቸው በሽታዎች የምንሰቃይ ምስኪኖች ነን ፤ እድሜያችን ያስተማረንን እንኳ የማናውቅ ።

ብዙ ያልተጠየቅናቸው ጥያቄዎች አሉብን በግዜ ሂደት ህመም እየሆኑ እኛነታችንን ከእግዜር የነጠሉ

ብንጠየቅም
ደሞ መልስ የማናገኝላቸው ሺህ ጥያቄዎች ...

እኔ እድሜዬ መዳብ የሆነብኝን ወርቅ ከሔደ ደግሜ እንደማላገኝ አስተማረኝ..እናንተስ

ሔኖክ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

27 Jan, 19:05


አንድ በእድሜ ብዛት የጫጨ አዛውንት አልጋ ላይ ሊሞት እያጣጣረ ነው።

✔️አምስት የቤተሰቡ አባላት ቆንጅዬ ሚስቱና አራት ልጆችሁ ከአልጋው አጠገብ ቆመው የማይቀረውን ሞት እየጠበቁ ነበር።

✔️ ከልጆቹ መካከል ሦስቱ ታላላቆች ረጃጅሞች፣ ቆንጆዎች እና አትሌቲክስ ነበሩ፤ ነገር ግን አራተኛውና የመጨረሻው ልጅ የቤተሰቡ አስቀያሚ ነገር እንደነበር ጥርጥር የለውም።

ባልየው በሹክሹክታ "ውድ ሚስቴ ትንሹ ልጅ በእውነት የእኔ መሆኑን አረጋግጭልኝ። ከመሞቴ በፊት እውነቱን ማወቅ እፈልጋለሁ ሃቅ ከነገርሽኝ ይቅር እልሻለሁ" ሚስትየው በእርጋታ አቋረጠችውና "አዎ የኔ ውድ በፍፁም ምንም ጥያቄ የለውም በእናቴ መቃብር ላይ እምላለሁ አባቱ አንተ ነህ" አለችው። ሰውየው በመጨረሻ ለብዙ አመታት ያስጨነቀውን ጥያቄ በመጠየቁ ደስተኛ ሆኖ ሞተ።

ውድ ባል ትንፋሹ ፀጥ ካለ በኋላ ሚስትየው ቁና ቁና እየተነፈሰች "ፈጣሪ ይመስገን ስለ ሶስት ታላላቆች አልጠየቀኝም" 🤦🏼‍♀

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

27 Jan, 07:14


ባለቅኔ ነበርኩ
ባለኝ ሰዓት ቅኔ
ያ...ኔ!

ቅኔ ይሏት እርግብ
አፍኜ ስመግብ
ስታዜም ስሰማት
መዝሙሯን ስቀማት
ቀምቼ ሳፏጨው
የሷን እየቀዳሁ፡ አድማስ ላይ ስረጨው፤
የሰማ ታማሚ፡ መስሎት የፈለቀኝ
ወደኔ እየመጣ፡ ፈውስ ሲጠይቀኝ፤
እሷ የምትለውን፡ ስሰማ ሳቀብል
ከሷ የሚፈሰውን፡ ስቀዳ ሳፀብል
የዳነው መስካሪ፡ ታምሬን ሲነዛ
ደጄን የሚናፍቅ፡ አማኝ እየበዛ
ለፀጋ ለስሜ፡ ሲመታለት ድቤ
በድንገት አምልጣኝ፡ በረረች እርግቤ።

ሄደች ከነድምጿ፡ በስም አስቀርታኝ
ሄደች ከነፈውሷ፡ ከገድሌ ጋር ትታኝ
የምበትንላት፡ ጥሬ ቀርቶኝ ከጄ
ቢረክስም በዜማ የፀደቀው ደጄ
በፈውስ ናፋቂ፡ ሰርክ ይጨናነቃል
ምስኪን! ኪን እርግቤ
እንኳንስ መሄዷን ፡መኖሯን ማን ያውቃል?

ብቻዬን አዘልኩት፡ አግኝቶ ማጣቱን
ጸጋው የተቀማ ፡ስም ሆኖ መቅረቱን
ማቃቴን አፍኜ፡ ብቻዬን ታመምኩት
በነበር ስወደስ ፡መቻልን ቃተትኩት፥

ግን አልሆነልኝም
አልጮህ ድምፅ የለኝም
ያድናቂዬ ድቤ፡ ዜማው ይበልጠኛል
አልጠፋ እንደርግቤ ማን ክንፍ ይሰጠኛል?
ታዲያ ከዚህ ስቃይ፡ ማን ያስመልጠኛል?

እውነት!

ባለቅኔ ነበርኩ፡ ያ...ኔ!
ቅኔ ይሏት እርግብ፡ እያለች ከጎኔ
ዜማዋ ሲያደምቀኝ ትንፋሿ ሲሞቀኝ
አርፎ እንደማጣጣም፡ እየቀዳሁ ስቀኝ
ያየ ሲያጨበጭብ፡ የሰማ ሲያደንቀኝ
ስጨምቃት ተጨንቃ የምታስጨንቀኝ
አንድ እርግብ ነበረች፤
አሁን ግን የለችም!
ለጠየቀኝ ሁሉ ፡እሺ ስል በርራለች።

ልክ እንደዛ ተረት፡ የልጅ መጫወቻ

ባለቅኔ ነበርኩ፡ አሁን ግን ፍራቻ
ሁሉን ነገር ላጣው፡ የቀረኝ ስም ብቻ።

Red-8

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

26 Jan, 20:00


አንዳንድ ነገሮችን መቀየር አልችልም።ለምሳሌ አንቺን ማፍቀሬ ስዕተት መሆንን እያወኩ እንኳን ፍቅሬን ማስቆም አልቻልኩም ነበር።ምክንያቱም ከባዷ እጣፋንታዬ በአንቺ ህይወት መካካል አቅም-አጥታ ወደቃ ነበር.......

ጓደኞቼ ጠየቁኝ.....ቤተሰቦቼም በደምብ ጠየቁኝ....ሁሉም ወዳጆቼ የምር እንዳፈቀርኩ ማመን ፈልገው ነበር......ያ ዝምተኛው ሰው፤ያ ከክፍሉ የማይወጣው ሰው፤ያ አይናፋሩና ሴቶችን ማውራት በጣም የሚከብደው ሰው ያፈቅራል ብለው አላሰቡም ነበር።

ግን የሆንኩትን የማውቀውና የምረዳው እኔ ብቻ ነበርኩ።ማንም ሰው ማፍቅር ስለፈለገና ስላልፈለገ እንደማያፈቅር ተረድቻለው።በሌሎች ማፍቀር የሚስቀው ሁሉ ነገ እሱም ተረኛ እንደሆነ አውቂያለው።ፍቅር ባልጠበቅነውና ባላሰብነው ጊዜ የሚመጣ ከባድ ነገር መሆኑንም በደምብ ተገንዝቢያለው......ስለዚህ ፍቅር ወደደንም ጠላንም እኛ ስለፈለግንና ስላልፈለግን የሚሆን ሳይሆን እንደ ድንገት የሚከሰት ምትሃታዊ ሀይል ነው።

(ከአንቺ ፍቅር እንደማይዘኝ ያጣጣልኩት እኔ አንቺን ያፈቀርኩበት የማይታመን ጊዜ)

(Unreal)
✍️ Bemni Alex

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

26 Jan, 10:12


ከቴሌግራም መንደር ያገኘሁት አስተማሪ መልእክት!!
____
እናቴ ጎረቤታችንን ጨው እንዲያውሷት ስትጠይቅ ሰማኋት፡፡ እኔም በመገረም

"እናቴ በቤታችን እኮ በቂ ጨው አለ፤ ታድያ ለምን ጠየቅሻቸው"

አልኳት፡፡ እናቴም እንዲህ አለችኝ

"እነሱ ሁሌም የተለያዩ ነገሮችን ከኛ ይጠይቁናል፤ እንደምታውቀውም ድሀ ናቸው፡፡ ስለዚህ እኔም እነሱን ብዙ የማይጎዳ ነገር ለመጠየቅ አስቤ የመጣልኝ ነገር ጨው ነው፡፡

◆ይህን ያደረኩት እነሱ ላይ ጫና ለመፍጠር ሳይሆን፤ እኛም እንደምንፈልጋቸው እንዲሰማቸው ብዬ ነው፡፡ በዚህም የፈለጉትን ነገር እኛን ያለ ሀፍረት በቀላሉ መጠየቅ እንዲችሉ ያደርጋቸዋል ብዬ በማሰብ ነው፡፡"አለችኝ……

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

25 Jan, 11:01


📚ርዕስ:- የሳጥናኤል ጎል ኢትዮጵያ!! ቁጥር አንድ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

24 Jan, 06:14


#የመጻሕፍት_ስጦታ_ኩፖን
ለወዳጆ የመጽሀፍ ስጦታ መስጠት አስበዉ ምን አንደሚገዙ ግራ ገብቶዎታል?
አያስቡ ከኛ በፈለጉት መጠን ኩፖን በመግዛት ላሻዎት ሰዉ ኩፖኑን መስጠት ይችላሉ፣ እነሱም የወደዱትን መጸሀፍ ከ ጃዕፈር መጸሀፍት በመሄድ ያሻቸዉን መጸሀፍ ሸምተዉ መመለስ ይችላሉ ።

ጃዕፈር መፅሀፍት

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

22 Jan, 17:37


ካልሰማችሁ "Data is the future currency"። ሀገራት ከጊዜያት በኋላ የሚወዳደሩትም የሚገዳደሩትም ባላቸው dataset ይሆናል ማለት ነው። ለዚህም ሲባል ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው ትላልቅ ሀገራት የራሳቸውን " Data monopoly" ለመፍጠር የሚታገሉት።

ቻይና መሰረቱ አሜሪካ የሆነውን ፌስቡክ መጠቀም አትፈልግም ምክንያቱም ቻይናውያን ፌስቡክ ተጠቀሙ ማለት አሜሪካ በቻይና ፖለቲካም ሆነ ኢኮኖሚ ላይ አሻጥር መስራት ብትፈልግ የተጠቃሚዎችን interest በደንብ ስለምታውቅ ጉዳዩ ውሃ የመጠጣት ያክል ቀላል ነው።  ለእውነት የቀረበ የውሸት ዜና አቀነባብራ የቻይናውያንን ሀሳብ ማስቀየር ቻለች ማለት ነው።

ሌላው እነዚህ giant tech companies ትልቅ ኢኮኖሚ ያንቀሳቅሳሉ። ፌስቡክና ዩቲውብ ይከፍላል አይደል? (እኛን ሽጦ እኮ ነው 😃)
እነዚህ የሶሻል ሚድያ ፕላትፎርሞች የተጠቃሚዎችን ፍላጎት በየጊዜው ያጠናሉ። ምን እንደምንጠላ ምን እንደምንወድ ያውቃሉ።

ስለዚህ የኛን ፍላጎት ፍላጎታችን. ለሚፈልጉ በመሸጥ ሀብት ያካብታሉ። ለድሆች የሚሆን ምርትን መሸጥ ለፈለገ ድሆችን መርጦ ማሳየት፣ ለሴቶች መሸጥ ለሚፈልግ ሴቶችን ብቻ መስጠት ለነ ፌስቡክም ሆነ ቲክቶክ ቀላል ነው።

የሶሻል ሚድያዎች ስራ የማንኛውንም ግለሰብ አካውንት በደንብ በማጥናት የግለሰቡን ኮፒ ሰርቨራቸው ላይ መፍጠር ነው። ለምሳሌ የኔን ኮፒ መፍጠር ሲፈልጉ የምወደውን ምግብ፣ ሰው፣ የማየውን የፊልም አይነት፣ የሚመቸኝን የሰው ባህሪ፣ ጫማ፣ ልብስ እያለ ሁሉንም ነገሬን ከምሰጠው data እና ፕላትፎርሙ ላይ ባለኝ እንቅስቃሴ በመረዳት ጠንቅቀው ለመረዳት ይሞክራሉ። ያገኙትን ዳታ አቀነባብረው ስለኔ ያላቸውን መረዳት ያሻሽላሉ።

ቲክቶክ ተጠቃሚን በመረዳት ረገድ ከሌሎቹ የተሻለ algorithm አለው። ይህ ደግሞ ቻይናን የዳታ ባለሀብት የማድረግ ትልቅ አቅም አለው ማለት ነው። አሜሪካ በነ ጎግልና ፌስቡክ ስታደርገው የነበረውን ነገር ቻይና በቲክቶክ አሻሽላ ስትመጣ  ስጋት አድሮባታል። ቲክቶክ የአሜሪካውያንን ዳታ ያስቀመጥኩት እዛው አሜሪካ ቴክሳስ ነው ቢልም የሰርቨሩ back up ግን ሲንጋፖር መሆኑ ጋር ተደማምሮ ቲክቶክ ለአሜሪካ ስጋት ሆኖባታል።

Tiktok በአሜሪካ ባለፈው አመት(2024) ብቻ  12.34 ቢሊዮን ዶላር አትርፏል። በአንጻሩ ፌስቡክ በቻይና የተዘጋው 2009 ላይ ነበር። ሜታ በሌሎች ፕላትፎርሞቹ በ2013.49 ቢሊዮን ዶላር ማትረፍ ችሎ ነበር (businesses insider)

ድጂታላይዜሽን ከተለመደው የሀገራት import/export እና ሚሊተሪ አቅም ባለፈ ሌላ  መለካኪያ አምጥቷል እላችኋለሁ

© ብርሃን ነጋ
አብረሆት ላይብረሪ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

22 Jan, 08:54


በሕይወት ሕግ ሁሉም መገናኘቶች መለያየት እንዳላቸው ሳስብ ይዘገንነኛል ፤ እሷ ከኔ መለየት እንኳ ባትፈልግ የሆነ ቀን ሞት በተባለ ጨካኝ አረመኔ ወይ እሷ ወይ ደሞ እኔ እንወሰዳለን በቃ ሁሉ ነገር ግዜያዊ ነው

አቤት ሰው ግን ይህን እያወቀ እንዴት መልካም ማድረግ ይሳነዋል (የኔው ለኔ ጥያቄ ነበር )
እንደውም አንዳንዴ የሰው ልጅ ዘላለማዊነትን የሰነቀ ግዜያዊ ፍጡር ይመስለኛል

✍️ ሔኖክ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

21 Jan, 16:51


ፍቅረኛ ለመያዝ ቀና ልብ ይፈልጋል። ከዛ ደግሞ አስተዋይ መሆን አለብን። ምክንያቱም ዘው ብለን የምንገባው የሰው ህይወት ውስጥ ነው።

ስንወጣ ደግሞ የሰውን ልብ እና ቅስሙን ሰባብረን... ህይወቱን አመሰቃቅለን ... ስሜቱን ጎድተን ተስፋ አስቆርጠን ነው የምንወጣው።

ይህን ሁሉ በደል ከማድረሳችን በፊት እስክንበስል ፍቅረኛ አንያዝ።

- ይኸውልሽ <አርግዣለሁ > ብለሽ ፍቅረኛሽን የመፈተን እድሜ ላይ ካለሽ ፍቅረኛ ይቅርብሽ።

ምን አድርጌ ላስደስተው ብሎ ከመጨነቅ ይልቅ ምን ብዬ ላስጨንቀው የምትይበት እድሜ ላይ ከሆንሽ ይቅርብሽ።

የእንትና ባል ለሷ እንዲ ያደርጋል አንተ ግን... ምናምን የሚል አስተሳሰብ ላይ ከሆንሽ ገና አልበሰልሽም።

ፍቅር ማለት ካፌ ለካፌ ሬስቶራንት ለሬስቶራንት መንከራተት መስሎ የሚሰማሽ ከሆነ በቃ ይቅርብሽ።

ፍቅሩን የገለፀልሽን ቴክስቶች ለሴት ጓደኞችሽ በማሳየት <እኔ እኮ እስከዚህም ነኝ .. > ብለሽ የማውራት ሞራል ላይ ከሆንሽ ይቅርብሽ።

- ይኸውልህ። ስለፍቅረኛህ ለጓደኞችህ መናገር የምታፍርበት ጊዜ ላይ ከሆንክ ተወው ፍቅረኛ አትያዝ።

<እኔ እኮ ለሷ እስከዚህም ነኝ ስለምታሳዝነኝ ነው ወይ ደግሞ እሷ ናት በደንብ የምታፈቅረኝ > ብለህ የምታወራበት እድሜ ላይ ካለህ አታፍቅር።

አውቀህ ስልክ አለማንሳት ... ሚስኮሎቿን ለጓደኞችህ ለማሳየት የምትጣጣር እድሜ ላይ ካለህ ይቅርብህ። ጊዜ ያለመስጠት ...

የማስቀናት... ሌላ ሴት የመደረብ ሞራል ላይ ከሆንክ ገና ስለሆንክ ፍቅረኛ አትያዝ።

ስንት ልቦች የተሰበሩት... ስንት ተስፋዎች የተቆረጡት ...ስንት ቤቶች የተዘጉት ... ስንት ህይወቶች የጠፉት በግዴለሽ ፍቅር ነው።

ፍቅርን ሁሉም ሰው ይፈልገዋል። የሰው ልጅ ሁሉ ይፈልገዋል። ግን በግዴለሽ አፍቃሪ ነን ባዮች አጥተውታል።


ሰው ሁን ከሰውም ሰው ሁን

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

21 Jan, 12:58


ጥገኛን ተውና ታታሪውን አሳድገው!

የሆነ ጊዜ የዩናይትድ አረብ ኤመሬትስ መስራች ሼህ ረሺድን ኢንተርቪው አድርጌው ነበር። ስለነገዋ ዱባይ ስጠይቀው የሰጠኝ መልስ አስገርሞኝም አስደንቆኝም ነበር

ምን አለ?

"አያቴ ግመል ይጋልብ ነበር፣ አባቴም ግመል ይጋልብ ነበር፣ እኔ ደግሞ መርሰዲስ እየነዳሁ ነው። የኔ ልጅ ላንድሮቨር ይነዳል። የልጅ ልጄም እንደዚያው ላንድሮቨር ይነዳል። የልጅ ልጅ ልጄ ግን ግመል መጋለቡ አይቀሬ ነው!"

"ለምን ?"
ለምን ካልከኝማ!

"ክፉ ጊዜ ጠንካራ ሰዎችን ይፈጥራል። ጠንካራ ሰዎች ደግሞ ሁሉ ነገር ቀላል የሆነበትን ጊዜ ይፈጥራሉ።ቀላል ጊዜያት በተራቸው ደካማ ሰዎችን ይፈጥራሉ። ደካማ ሰዎች ደግሞ ክፉ ጊዜን መልሰው ያመጡታል። ብዙዎች አይገነዘቡት ይሆናል ፣ ነገር ግን ይህ እንዳይመጣ ታታሪዎችን ማሳደግ አለብን። ያ ሲሆን ጥገኞች አይፈጠሩም።"

By Melaku Berhanu

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

20 Jan, 17:44


ለአንዳንዶቻችን ህይወት እቅፍ አበባ ይዛ አልጠበቀችንም...እሾኹ ነው የደረሰን።


ከ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

19 Jan, 06:53


ነግሬሽ ነበር?

ደመና ቀን እንደማልወድ? ካፊያ እንደሚጨንቀኝ ፣ ዝናብ ድብርቴ እንደነበር? ደሞም ተራ ሁነት – ተጠልዬ ፣ ኮት ደርቤ የማሳልፈዉ።  

ይግረምህ ሲል ጥላ ጨብጠሽ ፥  ዝናብ ላይ አጊጠሽ ካየሁ ወዲህ ክረምት ናፋቂ ሆኛለሁ። 

ተስፋ አይሰንፍ .  .  . ሃምሌ መሃል ወለም ላለኝ ልብ — ይኀዉ ጥር መሃል እታሻለሁ።


.

@samuel_dereje

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

18 Jan, 17:26


ነብስ የለኝም እዪኝ እስኪ
ስጋ ብቻ ትርኪ ምርኪ
አላውቅበት አለየሁም ፍቅርሽን ከጥላቻ
ጠዋት ማታ አንቺን ብቻ
ይኸው ዛሬም ሄደሽ አንኳ
ስመኝ አለው ያንቺን ታንኳ

HENOK

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

17 Jan, 08:12


#ሁላችሁም_ተጋብዛቹሃል
የፊታችን ጥር 12 ማለትም ሰኞ ሜክሲኮ ዋቢሸበሌ ሆቴል ስር የሚገኘዉ አዲሱ ቅርንጫፋችን በይፋ ስራ ይጀመራል።
በእለቱም ልዩ ቅናሽ፣አዲስ እና የቆዩ መጸሀፍቶችን አካተን እናንተን እንደምንጠብቃችሁ እየገለፅን የዚህ ልዩ እድል ተጠቃሚ ትሆኑ ዘንድ በ አክብሮት እንጠይቃለን ።

የንባብ ባህል እንዲዳብር እንተጋለን  !!

TelegramFacebook ● Instagram ● Tiktok ● Website

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

16 Jan, 21:56


ሌላ ሴት ልታገባ ያልክ ቀን እንኳ ብደውልልህ እሷን ትተህ እኔ ጋር ነው አይደል የምትመጣው? እለዋለሁ ሁሌ …. ፈገግ ብሎ ያየኝና “ደፋር ኮ ነሽ….ይለኛል።

ካለሁ ነገር ሁሉ እኔን አስበልጦ እንደሚወደኝ አውቃለሁ። ሲሳሳልኝ:ከራሱ ሲያስቀድመኝ: ሲጨነቅልኝ: ለኔ ሲኖር አይቻለሁ። ( በእርግጥ እንዲ ማለት ከባድ ይመስላል። እኔ ግን አይኑን ሳያርገበግብ : ይሄን ልጅ ግን ምን አስነክታው ነው እስኪባል የሚያውቁን ሁሉ እስኪገረሙ ድረስ ….ሳናድደዉ :ሳበሳጨው ችሎ በክፉ ቀናቶቼ ላይ ለደስታዬ ሲፈጋ: አብሮነታችንን ለማቆም ብዙ ሲለፋ አውቅ ነበር።)

ይመስለኛል የበዛ መውደዱ: የትም አይሄድም ብዬ እንዳስብ ለኛ እንዳልጨነቅና በተወዳጅነት ተኮፍሼ ለሚሰጠኝ መውደድና ክብር ትንሽ እንኳ አፀፌታን መስጠት የማልችል ሴት አደረገኝ።

ከዛ በአንዱ ቀን በትንሽ ነገር ተጋጨንና ….ሂድልኝ አልኩት። ለመነኝ:አስለመነኝ….ከቀልቤ መሆን ያልቻልኩት እኔ ግን ግድ አልሰጠኝምና ምንም እንደጎደለብኝ አልተሰማኝም። መሄዱ እንደሚያም: እንዴት እንደሚናፍቀኝ ለመረዳት ብዙ ረፈደብኝ።

ሄደ። ከዛ አልተመለሰም። ልመልሰዉ ሞከርኩ….መሄድ አለማምጄው ኖሮ መመለስ አቃተኝ።

እናማ አሁን የገፋሁት እኔ: ወዶኛል አይጠላኝም ያልኩት እኔ: በተራዬ እጅግ እየናፈቀኝ:እያመመኝ :እያስመሰልኩ አብሮነታችን ማክበር ያልቻልኩት እኔ … ሲያቅፈኝ ህይወት እንደሚቀለኝ: ችግሮቼን ችሎ ማሸነፍ ብቻን ያለማመደኝ እሱ እንደነበር:በጣም እንደሚናፍቀኝ :በጣም እንደማመሰግነው ያልነገርኩት እኔ የሄደበትን ቀን ሻማ እያበራሁ አከብራለሁ።

በስመአብ ጊዜው እንዴት ይሮጣል? አትመጣም በቃ?

By Ma Hi

💫ወግ ብቻ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

13 Jan, 16:30


ተወዳጁ ተዋናይ አማኑኤል ሐብታሙ  ቤቱ ደጅ ላይ ባለች መጠነኛ ሳጥን መጻሕፍትን ከአንዱ ወደሌሎች  ማስተላለፍ ከጀመረ ከራርሟል :: ይህ ድንቅ ዓላማ በደንብ መሰራጨትና መተዋወቅ ያለበት ጉዳይ ነው ::

በእውነቱ ይህ የተዋናይ አማኑኤል ሐሳብ  በየቤቱ ሼልፍ ላይ ሳያስፈልጉ እንዲሁ የታፈኑና የተጨቆኑ መጻሕፍትን ነጻ የሚያወጣ እና የንባብ ባህላችን እንዲዳብር ራሱን የቻለ አስተዋጽኦ የሚያደርግ ምርጥ መላ ነው ይዞ የመጣው ::  በነጻ ወስደህ ታነባለህ ያለህን መጽሐፍ ደግሞ አምጥተህ ትስቀምጣለህ ::

በምትመለከቱት የተዋናይ ሐብታሙ ደጅ ላይ ባለችው ሳጥን ውስጥ መጻሕፍት አሉት :: ውስጥ ያሉትን መጻሕፍት ወስዳችሁ ማንበብ ትችላላችሁ :: እንዲሁም ደግሞ ቤታችሁ የማትፈልጓቸው መጻሕፍት ካሉ እዚች ሳጥን ውስጥ ማስቀመጥ ትችላላችሁ ::

Source: Jafer Books

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

13 Jan, 08:24


ሁለት ራስ


"ወንድነቱን ተፈታተንኩት....".....አለችኝ ደንደን ብላ እየተቀመጠች....

"እንዴት...."...አልኳት ለመልሷ ጓጉቼ...

"provide እንዲያደርግ አልፈቀድኩለትም....protector እንደማያስፈልገኝ አሳየሁት...ገብቶሻል የምልሽ እኔ ለራሴ እንደምበቃ በተዘዋዋሪ ነገርኩት....ወንድነቱን ቀማሁት...."

"ለራስሽ መሆንሽ እኮ ደስ ሊለው ይገባ ነበር...."...አልኳት

"አይምሰልሽ....ወንድ ልጅ በተፈጥሮው protector or provider መሆን ያስደስተዋል....እኔ በጣም independent ስሆን አላስፈላጊነት ተሰማው....አልፈርድበትም ተፈጥሮው ነው....እርሱም አይፈርድብኝም የኖርኩት ህይወት በማንም ላይ እንዳልመረኮዝ አድርጎ ሰርቶኝ ነው....

ታውቂያለሽ ልጋብዝሽ ብሎኝ ተገናኝተን ካልከፈልኩ ራሴን እንደሚያመኝ.....

ተሳስቶ ፀጉርሽን ላሰራሽ እንዳይለኝ በየሳምንቱ በምቀያይረው human hair ለራሴ እንደምበቃ አሳየዋለሁ....ልብሴን በቀን ሁለቴ ስቀይር ፊቱ ላይ ድንጋጤውን አየዋለሁ....ቋሚ ጠረን እንኳን የለኝም....ሽቶ እየቀያየርኩ አፍ ሳይወጣኝ በጠረኔ ብቻ ለራሴ በቂ ነኝ  እለዋለሁ.....

ለመጀመሪያ ጊዜ መኪናው ውስጥ እንድገባ በኩራት ሲጋብዘኝ ወደ መኪናዬ ጠቁሜው ምግብ የምንበላበት ቤት እንዲከተለኝ ስነግረው ኩራቱ ሲረግብ በአይኔ አይቼዋለሁ....."


"መጨረሻ ላይ ምን እንዳለኝ ታውቂያለሽ"

" 'ራሴን የማግባት እቅድ የለኝም'....ብሎኝ ነው የሄደው....ተፈጥሮን አትጋፊውም....ልክ አልነበርኩም....ሌላው ቀርቶ አለሁልሽ እንዲለኝ እንኳን ፈቅጄለት አላውቅም...ማልቀስ ብፈልግ እንኳን በሬን ዘግቼ ነው የማለቅሰው....ለአመታት ያለከልካይ ሳነባ እርሱ አያውቀኝም....አይዞሽ ለመባል ድምፄን ጮክ አድርጌ ሳለቅስ እርሱ አያውቀኝም....አየሽ እዚች ጋር ተላለፍን....


ወንድ የቤት ራስ አይደል....ሴት ደግሞ ሰውነት....ራስ ያለ ቀሪው ሰውነት...ከአንገት በታች ያለውም ሰውነት ያለ ራስ ምንም ናቸው...ሁለት ራስ ቢኖር ያለሰውነት ምንድን ነው....?....አየሽ ሁሉም የተሰጠውን character በአግባቡ ሲጫወት ነው ተውኔት የሚያምረው.....ልክ አልነበርኩም....የኖርኩት ህይወት ልክ ባልሆነ መንገድ ሰራኝ"

"ህመም አሞ ብቻ ቢተው ጥሩ ነበር....በታመምሽው በኩል አጥር ስታበጂ ትኖርያለሽ....ከዛ የሆነ ቦታ ላይ ራስሽን ከራስሽ ጋር ብቻ ታገኝዋለሽ"....


የምላት አጣሁ....ራስን ከራስ ጋር ብቻ ማግኘት ስሜቱ ምን ምን ይል ይሆን...እንጃ  ።

Shewit

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

11 Jan, 07:46


በነገራችን ላይ በተመደብኩበት የፋብሪካው ክሊኒክ ውስጥ አብሬያቸው ስሰራ ከነበሩት ባልደረቦቼ መኻከል በጽዳት ሰራተኝነት መደብ ያገለግሉ የነበሩት የሀገሪቱ መሪ ሊቀመንበር መንግስቱ ሀይለማሪያም እህት አመለወርቅ ሀይለማሪያም አንዷ ነበሩ ....አመለወርቅ ሴት ከመሆናቸው በቀር ሁሉ ነገራቸው የወንድማቸው አምሳያ ናቸው .. መልካቸው ፍፁም አያሳስትም..አነጋገራቸው ሁኔታቸው ሁሉ ቁርጥ ጓድ መንግስቱን ነው ሲናገሩ አይኖቻቸውን ወዲያ ወዲህ እያደረጉ ቃላትን ጠበቅ ጫን ያደርጋሉ። ደፋር ናቸው የመሠላቸውን ያመኑበትን ከመናገርም ከማድረግም ወደ ዃላ አይሉም .. ሀሳባቸውን አፍታተው የመናገር ችሎታቸው አስገራሚ ነው.. ከሁሉም በላይ የተመደቡበትን የፅዳት ስራ አክብረውና በትጋት በመስራት የሚያክላቸው የለም...የመንግስቱ እህት ነኝ ብለው አይመፃደቁም.. ብዙዎች የመንግስቱ እህት ሆነው የፋብሪካ ሠራተኛ ያውም የፅዳት ሰራተኛ መሆ መሆናቸውን አምነው መቀበል ይቸግራቸዋል!..

[ ከማዕበል ማዶ፣ ገፅ 120 -ተስፋዬ ወንድምአገኘሁ]


~
Zeraf books

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

10 Jan, 07:16


እንደማንም ሰው ነኝ ስጋ እንደለበሰ፣
ሹመት ማዕረግ አልቦ የተግበሰበሰ።

#BamU

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

09 Jan, 18:56


እንደምንለያይ አውቃለኹ ፤ ነብይ ሆኜ ሳይሆን በቃኝ የማታውቂ ፥ ፍላጎትሽ ሩቅ እንደሆነ ተረድቼሽ ነው...ልክ እንደ አዲስ አበባ ነዋሪ ቤቱ ዛሬ ይፍረስ ነገ እንደማያውቀው ፤ የሆነ ቀን የእኔና የአንቺ ነገር እንደሚያበቃ አውቀዋለኹ።


እስከዛ...
የቀደመው ፍቅራችንን እያሰብኹ አብሮነታችንን ባጣጥመው አስመሳይ ያስብለኛል?


ከ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

08 Jan, 15:27


ካጣት በሗላ መሻቷን ሳትነፍግ ስጣት ብሎ የፀለየው ትዝ ሲለው ፀሎቱን ሊያሰርዝ መፀለይ ጀመረ ፤ ምን የሚሉት ነዉ ብሎ ከግዜያት በሗላ መፀለዩን ተወዉ።

እያያት እንሔደችው እያያት አገባች እያያት ወለደች
Henok

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

06 Jan, 05:26


ሂሳብ ስለማልችል ሳቀብኝ....ግጥም መፃፍ ስለማይችል ሳቅኩበት😴



ስለ mathes እውቀቴ ቅድም ተናግሬያለሁ🙄....ከዚሁ ድባብ ሳልወጣ በአንድ አጋጣሚ የተማርኩትን ትምህርት ላውጋችሁ....prep እያለሁ በአማርኛ ክፍለጊዜ አርፍዶ የገባ ተማሪ ርዕስ ይሰጠውና ግጥም ወይ አጭር ድርሰት ፅፎ ክፍለጊዜው ሊያልቅ ሲል እንዲያቀርብ ይደረግ ነበር....

ለኔ ባይጎረብጠኝም አብዛኛው ተማሪ ይጨነቅ ነበር....እንደውም ፈታ ብዬ የማረፍደው በእሱ ክፍለጊዜ ነበር(ፅሁፌን የሚሰማኝ ስላልነበር ይሄ ለኔ መድረክ ነበር😂)....

እናላችሁ የሆነ ከፈሱ የተጣላ ተማሪ ነበር...በቃ በትምህርት ፍቅር ያበደ....(በ7ተኛው ክፍለ ጊዜ physics ተምረን አስተማሪው ሊወጣ ሲል እጅ አውጥቶ ጥያቄ የሚጠይቅ....እንደውም አንድ አንዴ አስተማሪው ባላየ ያልፈው ነበር😂)...እና እሱ ልጅ mathes አላስኮርጅም ይለን ነበር....አትደንግጡ እና ባዶ ወረቀት ልስጥ እየተሳሰብን እንጂ🤷‍♀....


Maths ጥያቄ ስሪ ብሎ አስተማሪ ሲያፋጥጠኝ ስርበተበት በጣም ይቀልድብኝ ነበር....እና በአንድ የተባረከ ቀን ይሄ ልጅ በአማርኛ ክፍለ ጊዜ አረፈደ....የእኔ መዳኒያለም ምን ይሳነዋል ግጥም ፅፎ እንዲያቀርብ ተፈረደበት😂


ሙሉ የግጥሙን part ባላስታውስም አሁንም ድረስ ያልረሳሁት እና ቤት የመታ ሁለት ስንኝ አለ....😁

"እኔ ባንቺ ፍቅር የምሆነው ሳጣ
ምናለበት ፍቅርሽ ልቤ ላይ ቢንጣጣ"....

በቃ  I can't😂....በቃ አሳሩን አበላሁት...በቃ ሙድ አንዴ ነው ፍቺ ተብዬ በሽማግሌ ነው የፈታሁት.....


እና The lesson was "በሰው ድክመት እና በራሱ ችሎታ የሚኮፈስ ሰው የማይችለው ላይ ይጥለውና ማጣፊያው ያጥረዋል.... ሁሉንም ይችላል ያልነው ሰው እሱም የማይችለው አለ....and for every action there is equal and opposite reaction life ላይም ይሰራል"






ይመቻችሁ✌️
✍️ ከእለታት

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Jan, 19:45


✳️ ልሞት ስል የምተገብረው እቅድ 😁! ✳️

"ይገርምሃል በዚህ ምድር ማንም ሰው አቅዶት የማያውቀውን አንድ እቅድ አቅጃለው " አለኝ ፈላስፋው በእውቀቱ ። መፈላሰፍ ስለሚወድ 'ፈላስፋው' የሚል የማእረግ ስም ሰጥቼዋለሁ ። አንዳንዴ እንደ ጓደኛዬ ሳይሆን እንደ ትልቅ ሰው አንዳንዴም እንዳበደ ሰው አየዋለሁ ። ዛሬ ደግሞ በምድራችን ማንም ሰው አቅዶት የማያውቀውን እቅድ አቅጃለው ሲለኝ የተለያዩ ጥያቄዎች አእምሮዬ ውስጥ ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ ። ነገር ግን ያን ሁሉ ጥያቄ ከመጠየቄ በፊት እቅዱን ልስማ በማለት " ምንድን ነው እቅድህ ? " ስል ጠየኩት ። " ይገርምሃል " አለኝ በእውቀቱ ፣ ቀጠለና " ይህንን እቅድ እስካሁን ካሰብኳቸው እቅዶች በጣም የተለየ ነው ። የተለየ የሚያደርገው ደግሞ ልክ ልሞት ስል የምተገብረው ስለሆነ ነው  " አለኝ ቆፍጠን ብሎ ። ምን አልኩ ለራሴ 🤔 ??? ........... ለነገሩ እንዲህ ቢል አይገርመኝም ፣ በኔ እና በሚቀርባቸው ጓደኞቹ ፊት እብድነቱ በወረቀት እና በማህተም አይረጋገጥ እንጂ እንዲሁ የታወቀ ነው ። እኔ ብቻ ነኝ እንደውም እንደዚህ አይነት ፍልስፍናውን የማዳምጥለት ፣ ሌሎቹ ከቁጥር እንኳን አያስገቡትም ። ወደ ዛሬው ስመጣ ደግሞ እቅድ አለኝ ያለው ምንም አላስገረመኝም ። ምክንያቱም ማንም ሰው እቅድ ይኖረዋል ። እቅድ የሌለው ሰው እንኳን ቢሆን አንድ አባባል ለርሱ አለ ፣ "if you are not planning then you are planning to fail " ። እቅድ ማውጣቱ ሳልይሆን ያስገረመኝ እቅዱን ሊሞት ሲል የሚተገብረው መሆኑ ነው ። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ? ማንም ሰው የሚሞትበትን ቀን ሊያቅ አይችልም ። ስለዚህ ልሞት ስል እደዚህ አደርጋለሁ ማለት ከሞኝነት አስተሳሰብ ውስጥ ይመደባል ባይ ነኝ ። ታዲያ የጓደኛዬን እቅድ ስሰማ ምን ለማለት ፈልጎ እንደሆነ የበለጠ ለመረዳት " አልገባኝም አልኩት " ። "ምን ማለት ነው አልገባኝም ማለት ? ይህ እኮ ቀላል አማርኛ ነው የተናገርኩት ፣ ልሞት ስል የምተገብረው እቅድ አለኝ !" አለ ትንሽ ቆጣ ከዛም መጨረሻ ላይ ትንሽ ፈገግ ብሎ ። እኔም ተክትዬ "ያልገባኝ እኮ እሱ ነው ። እንዴት ነው ልሞት ስል የምተገብረው እቅድ አለኝ ልትል የምትችለው ? ማንም ሰው ቢሆን የሚሞትበትን ቀን ማወቅ አይችልም ፣ እንዴ ... ቆይ አሁን ብትሞትስ ? እቅድህን ሳትተገብረው ልትሞት ነው ማለት ነው ? " አልኩት ምን ሊመልስልኝ ይሆን ብዬ እያሰብኩ ። "ሰውዬ አልሰማህም መሰለኝ " አለኝ ትንሽ ፈገግ ብሎ " ልሞት ስል የምተገብረው እቅድ አለኝ ነው እኮ ያልኩህ ! አሁን ከሞትኩኝ አሁን እቅዱን ተግብሬ ነው የምሞተው " አለኝ ። .... " አይይይይይ በቃ ለየለት ማለት ነው " አልኩ በውስጤ ። ግን ለመኮነን ከመቸኮል መጀመርያ ሃሳቡ ምን እንደሆነ በደንብ ልረዳ በሚል ሃሳቤን ሰብስቤ "እስኪ በደንብ አስረዳኝ " ብዬው ማዳመጤን ቀጠልኩ ። " ምን መሰለህ አልዓዛር  ፣ በመጀመርያ የተናገርከው ነገር ትክክል ነው ። የሰው ልጅ የሚሞትበትን ቀን አያውቅም ፣ ነገ ይሁን ዛሬ ፣ ከዓመት በኋላ ይሁን ወይንም ከ10 ዓመት በኋላ ምንም የምናቀው ነገር የለም ። እኔም ለዚህ ነው ልሞት ስል የምተገብረው እቅድ አለኝ ያልኩህ ። ሞቴ ነገ ይሁን ዛሬ ፣ ከዓመት በኋላ ይሁን ከ10 ዓመት በኋላ ምንም የማቀው ፍንጭ የለም ። አሁን ላይ አንተን እያናገርኩ ሳለ እራሱ ላለመሞቴ ዋስትና የለኝም ። ይህ ማለት አሁን ልሞት እችላለሁ ማለት ነው ። ስለዚህ ልክ ልሞት ስል የምተገብረውን እቅድ እየተገበርኩ ነው ። አሁን እራሱ ከደቂቃዎች በኋላ መኖሬን ስለማላቅ እቅዴን እየተገበርኩ ነው " አለኝ ። ትንሽ ገብቶኛል  ፣ ግን ግራ ገብቶኛል ። ግን እቅዱ ምን እንደሆነ ስላጓጓኝ "እቅድህ ምንድን ነው ? " አልኩት በጉጉት ፊት ። አለመጸጸት ብሎ በአጭሩ መለሰልኝ ። እውነት ለመናገር የጠበኩት መልስ አልነበረም ። ትንሽ ግራ ቢገባኝም እንዲያብራራልኝ "ማለት እንዳልጸጸት ስትል ? " አልኩት ። " እየውልህ ምን መሰለህ ታሪኩ ፣ የሆነ ቀን  እንደለመድኩት አልጋዬ ላይ ትንሽ በጀርባዬ ጋደም ብዬ ማሰብ ጀመርኩ ። በመሃል ላይ ከየት እንደመጣ ባላቅም ስለሞት ማሰብ ጀመርኩ ። እርግጥ ስለሞት ስናስብ አብዛኛውን ሰው የሚታወሰው ከመቃብር በኋላ ወደየት ነው የምሄደው ብሎ ነው ። እኔ ግን በተቃራኒ ለማሰብ ብዬ ከመቃብር በፊት የሚኖረኝን ሁኔታ አሰብኩት ። የዛን ጊዜ የማደርጋቸውን አሰብኩ ። ይገርምሃል ፣ ልሞት አካባቢ የሚኖረኝን ሁኔታ ሳስብ መጥፎ የሚባል ሃሳብ በአእምሮዬ ውስጥ አልነበረም ። ሁሉም ጥሩ ማድረግን ነበር ሳስብ የነበረው ። ሲታየኝ የነበረው እናቴን ሂጄ ስላደረገችልኝ ነገር ሁሉ ማመስገን ፣ አባቴን ሄጄ ለከፈለልኝ መስዋዕት ሁሉ ምንም ማድረግ እንኳን ባልችል ሳመሰግን ፣ ሚስቴን ሄጄ እንዴት እንደምወዳት ገልጽ ፣ የተጣላሁትን ይቅር በሉኝ ብዬ ታረቅ ... ብቻ ምን አለፋህ ብዙ ጥሩ ጥሩ ሃሳቦች ሲመላለሱብኝ ነበር ። ነገር ግን አንድ ነገር ሳስታውስ ደነገጥኩኝ ። ለካስ አሁንም ልሞት እችላለሁ ? መቼ እንደምሞት ካላወኩት አሁንስ ላለመሞቴ ዋስትናዬ ምንድን ነው አልኩኝ ። አሁን የምማረው ትምህርት ፣ የምወስዳቸው ኮርሶች ፣ የምሰራው ስራ ፣ የምሯሯጥበት ቢዝነስ ሁሉም ከንቱ ሆነብኝ ። .... ልክ ይህንን እያሰብኩ እያለ በመሃል ስልክ ተደውሎ " አትመጣም እንዴ መኪና ይዤ እየጠበኩህ እኮ ነው " አለኝ ሹፌራችን ። ለካስ ለምርቃት እንደተጠራሁ ረስቼው ነበር ። መሄድ ባልፈልግም ግዴታዬ በመሆኑ ተነስቼ ሄድኩልህ ። ነገር ግን ከሃሳቤ ጋር የያዝኩት ፍልምያ አሁንም እንደቀጠለ ነበር ። የምርቃቱ ፕሮግራም ላይ በመታደም ሳለሁ የምግቡ ሰአት አልቆ የጭፈራው ሰአት ደረሰ ። በመሃል ይህ እንደወጀብ የማያልቀው ሃሳቤ ጥያቄ እንዳነሳ አደረገኝ ።  ግን ለምንድን ነው የሚጨፍሩት አልኩኝ ? ልጅቷ ስለተመረቀች ? ትምህርቷን ስለጨረሰች ? ወይስ 3 ፣ 4 ወይም 5 ዓመት ዩንቨርስቲ ቆይታ በመምጣቷ ?  ቆይ አሁን ሰው ትምህርት ተምሮ ስለጨረሰ ምኑ ያስደስታል ? ገና በተማረው ነገር ፍሬ ሳያፈራ ??? ይህ ማለት እኮ አትክልትን ፍሬ ሳያበቅል የዚህ አትክልት ፍሬ ይጣፍጣል እንደማለት ነው ። ቆይ ፍሬ ማፍራቱን ተዉትና ትምህርቱን በወጉ ይዛዋለች የሚለው እራሱ አሳሳቢ ነው ። ቆይ ማን ይሙት ? አሁን 10 ጥያቄ ከተማርሽው ልጠይቅሽ ብላት ከአባቷ ገዳይ አንድ አታደርገኝም ብለህ ነው። እንደውም ቢቻላት በአናጣ አናቴን መታ ብትገላግለኝ ደስ የሚላት ይመስለኛል ። ለነገሩ ምን በወጣት የምጠይቃት ? ለራሷ እዛ ዩንቨርስቲ በጥያቄ ቀቅልው ፣ ጠብሰው ነው የላኳት ። .... አሁን እሷን ትቼ ደግሞ ዳንኪራ የሚረግጠውን ህዝብ መታዘብ ጀመርኩ ። ሁሉም ነፍሱን አጥቶ በደመ ነፍሱ ነው የሚንቀሳቀሰው ። ከዚህ እንኳን ሞትን የሚያስብ ሰው ሊገኝ ቀርቶ ስለራሱ ጤንነት ፣ ደህንነት የሚያስብ ሰው የሚኖር አይመስለኝም ። ፀጥተኛ ፣ ጨዋ ፣ ጥሩ ሥነ ምግባር አላቸው ብዬ የማስባቸው ሰዎች ሳይቀር እግራቸውን ወደላይ እያውለበለቡ ሲጨፍሩ ሳይ በጣም ነው የምደነግጠው ። ጭፈራ ሞትን አይደለም መኖርን ያስረሳል ። ብቻ ከዚህ ሁሉ ትርምስና ጋጋታ በኋላ ወደ ቤቴ ተመልሼ የምወዳት አልጋዬ ላይ ጋደም አልኩኝ ። አሁን ግን ቅድም ሳስበው በነበረው ጉዳይ ላይ አንድ ውሳኔ መወሰን እንዳለብኝ አሰብኩኝ ። መቼ እንደምሞት የማላቅ ከሆነ አንድ ነገር እርግጠኛ ሆኜ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Jan, 19:45


መሞት እፈልጋለሁ አልኩ ...

...የቀጠለ

ይህንን ባልሰራሁ ብዬ የምቆጭበትን ነገር መስራት አልፈልግም ። ለምሳሌ ፣ አሁን የምሞት ከሆነ ማንንም ተሳድቤ አልያም ጎድቼ መሞት አልፈልግም ፣ አሁን የምሞት ከሆነ ፈጣሪ አዝኖብኝ እንድሞት አልፈልግም ፣ አሁን የምሞት ከሆነ እናትና አባቴን አስቀይሜ መሞት አልፈልግም ። እያንዳንዱ የምሰራቸው ስራዎቼ እኔን እና ፈጣሪን የሚያስደስቱ ፣ ወገኔን የሚጠቅሙ ናቸው ? ብዬ ማመዛዘን ይኖርብኛል ። ለምሳሌ የምማረው ወደፊት ስራ ለማግኘት ብዬ አይደለም ። ለምን ብትለኝ አሁን ላይ አስተሳሰቤ ተቀይሯል ። የምማረው ለማወቅ ስለምፈልግ ነው ! አዲስ ነገር ማወቅ ፣ አዲስ እውቀት ለመጨበጥ ፣ የአስተሳሰቤን አድማስ ለማስፋት ነው ። ሳጠና ለፈተና መሆን የለበትም ። ምክንያቱም ፈተና ሳልፈተን ብሞትስ ? ነገር ግን ቅድም እንዳልኩህ ለማወቅ ባጠና ፣ ሳልፍፈተን ብሞት እንኳን አይቆጨኝም ምክንያቱም በመጀመርያውም ለፈተና ብዬ ሳላላጠናሁ ! ስራ የምሰራ ከሆነም እንደዛው ። ለደሞዝ ብዬ የምሰራ ከሆነ ውሃ በልቶኛል ማለት ነው ። ደሞዝ አስፈላጊ ሆኖ ሳለ ግን ደሞዝ ሳልቀበል ብሞትስ ? ነገር ግን ለደሞዝ ብዬ ሳይሆን የምሰራው ፣ ስራው ስለሚያስደስተኝ ነው ! በስራዬ የሚጠቀሙ ሰዎችን ሳይ ደስ ስለሚለኝ ነው የምሰራው !  ለቢዝነስ ስሯሯጥ ከቢዝነሱ ዳጎስ ያለ ገንዘብ አገኛለሁ ብዬ አይደለም የምሰራው ። ቢዝነሱ ሳያልቅ ቢሞትስ ጸጸቱ ከመቃብር በኋላ እንኳን አይለቀኝም ። ነገር ግን ዋናው አላማዬ ገንዘብ ሳይሆን ስንት ነው በዚህ ስራ ይጠቀማል የሚለውን ነው የማየው ። እኔ ብሞት እንኳን የማይቆጨኝ ሃሳብ ነው ። አሁን እራሱ አንተን እንደዚህ ቆሜ በማናገሬ አሁኑኑ ብሞት አልቆጭም ምክንያቱም ለአንድ ሰው ያለችኝን አመለካከት አካፍዬ ነው የምሞተው ። ስለዚህ ወንድሜ በምታደርጋቸው ነገሮች ሁሉ የማትቆጭበትን ስራ ለመስራት ሞትህን ዘክር ! " አለኝ ። አፌን ከፍቼ ስሰማሁ ስለቆየሁ አፌን መለስ አድርጌ ከርሱ ጋት ያገናኘኝን ፈጣሪ በማመስገን ተሰናብቼው ሞቴን እያሰብኩ የኔስ ከመሞቴ በፊት የምተገብረውን እቅድ እያሰላሰልኩ ጉዞዬን ቀጠልኩ ።

------- Telegram Channel -------

👉 Astroግዕዝ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

02 Jan, 12:40


🦅 ሰላም

ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረው «ትዝታሽን ፡ ለእኔ ፥ ትዝታዬ ፡ ለአንቺ» በ 5ተኛ ልዩ እትም ከአንዳንድ ዕርማትና ከውብ የውስጥ ገጽ ላይ የሥዕል ንድፎች (illustrations) ጋር ለንባብ በቅቷል።

ከዚህ ቀደም ያነበባችሁትን፣ ሀሳብና አስተያየታችሁን የገለጻችሁልኝን ሁላችሁንም አመሰግናለሁ። ያነበባችሁት እና የወደዳችሁት ሰዎች ላላነበቡት ገዝታችሁ እንድታበረክቱት እጋብዛለሁ።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

31 Dec, 14:01


📌"ኢትዮ ኮሊዩድ" የተሰኘ ግዙፍ የፊልም መንደር በኢትዮጵያ ሊገነባ ነው።

ልክ "ሆሊዩድ፣ፖሊዩድ እና ኖሊዩድ" የፊልም መንደሮች ያለ ግዙፍ የሆነ "ኮሊዩድ ኢትዮጵያ " የተሰኘ የፊልም እና ኢኮ ቱሪዝም መንደር  በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በኮንታ ዞን ኤላ አንቻኖ ወረዳ  በጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ ውስጥ ከሪበላ ሀይቅ ዙሪያ ሊገባ እንደሆነ ተሰምቷል።

መንደሩ 43,000 ሺ ካሬ ካርታ በመረከብ አስገራሚ  በሆነው የዘንባ ጫካን ለዚህ አገልግሎት ለማዋል ስራ መጀመሩን አርቲስት  ወንድዬ ኮንታ ይፋ አድርጓል።

ይህ የፊልም መንደር እና የኢኮ ቱሪዝም ኢንዱስትሪ መንደር በውስጡ ፣የአርቲስቶች መኖሪያ መንደር፣ታላላቅ የፊልም አክተሮች እና የዘርፉ ሙያተኞች የሚገለገሉበት ሎጅ እና ማረፊያ ገስቶች ሀውሶች፣ አርት ስኩል የሙያ ኮሌጅ ፊልድ ሆስፒታል እና የባህላዊ ህክምና መስጫ ዞን፣ የሀይቅ ላይ የጀልባ መዝናኛ፣ የቱሪስት ካምፒንግ ሳይት እና መናፈሻ፣ የክሮማ ፣ የኤዲቲንግ፣ የሳውንድ ትራክ መቅረጫ እና ማቀነባበሪያ ስቱዲዮዎች የሲኒማ አዳራሾች፣ብሮድካስት የቴሌብዥን እና የሬድዮ ጣቢያ ፣ የሰርከስ ፣ የስዕል ጋለሪ እና የቅርፃቅርፅ  ፣ የመጻሕፍት ገበያ ማዕከል፣የባህላዊ አልባሳት ማምረቻዎች፣የዲዛይነሮች የጥበብ ውጤቶች፣የገበያ ማዕከልን ጨምሮ ሌሎችም ዘርፈ ብዙ  አገልግሎት መስጫን ያካተተ ነው ተብሏል።

አርቲስቱ የሚቆጠር ገንዘብ ሳይኖረው ትውልድን በሚያንፅ ሀገርን በሚያሻግር ድንግል ሀሳቡ የተማረኩ በገንዘብ የሚያግዙትን ባለሀብቶች ፣ ወዳጅ ጓደኞች ፣ የኪነ-ጥበብ ሙያተኞችን ከጀርባው በማሰለፍ   ግዙፉ ካምፓኒው በሁለት እግሩ እንዲቆም አስፈላጊውን ሁሉ ርብርብ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።

አርቲስት ወንድዬ ኮንታ ይህ ትልቅ ሀሳብ እንዲሳካ ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ያሉ የኢፌዴሪ ባህልና ስፖርት ሚኒስተርን እና የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ፐብሊክ ሰርቪስን ጨምሮ ሁሉንም ከልብ አመስግኗል።

ቶካ ፊልም መንደር እና ኢኮ ቱሪዝም ኃ/የተ/የግ/ማህበር በሚል ስያሜ የኢንቨስትመንት ሰርተፊኬት በማግኘት እና ሰፊ ይዞታ በመያዝ  ወደ ስራ ገብቷል ተብሏል።

ይህ ፕሮጀክት የኮንታ አከባቢን እንደብራዚሉ አማዞን ጫካ ከፍተኛ የዶላር ምንዛሪን እንዲያመጣና ዓለምአቀፍ የፊልም እና የቱሪዝም የገበያ ውድድር ውስጥ ለመግባት የሚያስችል ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር  የታሰብ ነው ተብሏል።

▬▬▬  ▬▬▬  ▬▬▬  ▬▬▬  ▬▬▬
➬ Open Reading | Rҽαԃιɳɠ Lιϝҽ Sƚყʅҽ !!

◎ የኢትዮጵያ አንባቢዎች ማህበር!
📚 የመጽሐፍት አፍቃሪያን ህብረት!

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

28 Dec, 20:05


መፅሐፍ መግዛት ስትፈልጉ @mexibooks ጎብኙ ። በኮሪደር ምክንያት ሱቁ ስለፈረሰ ፤ በዚህ ታገኙታላችሁ ። ሜክሲኮ አምደ መጻሕፍት | 0919370881 | 🙌 following @SostKilo . So the owner of the book store is called Eliyas, he is a vintage book collector of many years. He had a shop in Mexico but the corridor development has hindered his job. but he is active on calls and can sell old and classic books (including the first edition of the books and hard covers) starting from Amharic classic to English classic.

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

24 Dec, 17:35


"ቆይ ግን በምን ቋንቋ ብነግርህ ነው የምትሰማኝ” አለችው ኤፍራታ ተናዳ ...... "በወፍ" አላት ግማሽ ፈገግታን የቀላቀለ አሁንም ተስፋ የተሞላ ፊቱን እያሳያት “በቃ ተወኝ! እኔ አንተን አላፈቅርህም!” ..... “ግን እኮ ጓደኛሞች መሆን እንችላለን” አላት ሳሚ ፊቱ ላይ ምንም የመረበሽ ስሜት ሳይታይበት .... “አንችልም!”

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

23 Dec, 14:30


#BOOK_CLUB
📖ብቻችንን በማንበባችን ያጣናቸው ነገሮች ይኖሩ ይሆን?

ማንበብ ለአዳዲስ አለም እና ሀሳቦች በር ይከፍታል ነገር ግን በእነዚህ ገፆች ብቻችንን ስንጓዝ ጥልቅ ግንዛቤ እና ደስታ እያጣን ሊሆን ይችላል : :
ሀሳባችንን ለሌሎች ማካፈል ለመጽሃፍ ያለንን አድናቆት ያሳድጋል እና ልምዳችንን የበለጠ አርኪ ያደርገዋል።

የንባብ ልምዶቻችንን ማካፈል ያለውን ጥቅም ጥናቶች ያሳያሉ።

●ጥናት እንደሚያመለክተው ያነበቡትን የሚወያዩ ሰዎች ጽሑፉን በተሻለ ሁኔታ የመረዳት እና የማቆየት ችሎታ አላቸው (Murphy et al 2009)።
●በተጨማሪም፣ ስለ ጽሑፋዊ ልቦለድ ማንበብ እና ማውራት የሌሎችን ስሜት እና አመለካከቶች የመረዳት ችሎታችንን ሊያሻሽል ይችላል (Kidd & Castano, 2013)።

●በንባብ ቡድኖች ውስጥ መሳተፍ ወደ ማህበራዊ ትስስር እና የማህበረሰብ ስሜት ይጨምራል (The Reading Agency, 2015)።
●የጋራ ንባብ የድብርት ምልክቶችን ይቀንሳል እና አጠቃላይ የአእምሮ ጤናን ያሻሽላል (Billington እና ሌሎች፣ 2010)።

Jafar books

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

09 Dec, 07:55


አንቺ ላይ ያደረኩት በደል ብዙ ነው፤እውነት ቃላት ለማሳመር አይደለም...ከልቤ አሳዝኖኛል።እንዳንቺ የምወደው ሰው ያለ አይመስለኝም፤ይበልጥ የሚያሳዝነው ግን እንዳንቺ የከፋውበትም ሰው የለም።አብሬሽ ስሆን ይሄን ሁሉ እዘነጋለው፤በደሌ አስመርሮሽ ስትሸሺኝ...ጥፋቴ ገብቶኝ ለይቅርታ አልከተልሽም እኔ ይበልጥ እሸሻለሁ።
...የአስቴርን ዘፈን ስሰማ አንቺ ለእኔ ያዜምሽው ይመስለኛል <<ራሱ በድሎ ራሱ አለቀሰ...>> እያልሽ።

ይበልጥ የሚሰማኝ መቼ እንደሆነ ልንገርሽ?

አንቺ የሆንሽውን መቀበል አቅቶኝ፤እኔ የምስላትን አይነት ሴት ካሆንሽ ብዬ አስጨነኩሽ።ስለምትወጂኝ ላንቺ አልከበደሽም ሁኚ ያልኩትን ሆንሽ...እንደዛም ሆኖ አልበቃኝም።
ይሄን ባሰብኩ ጊዜ መንፈሴ ይታወካል።አንቺ ከበቂ በላይ መሆንሽ ዘግይቶ፤የሌላ ከሆንሽ በኋላ እንደገባኝ ሳስብ...ፀፀት እጆቼን የኋሌት ያስረኛል፣ወፍራሙ በጎነትሽ እንደ ጅራፍ ይገመዳል፣አመለ ቢስነቴ፤ጥጋቤ እሾህ ይሆኑ እና ትዝታ በፈርጣማ ክንዱ ይገርፈኛል።

ልትሄጂ ስትይ እጅግ አዝነሽ የጠየቅሽኝ ጥያቄ ህሊናዬ ውስጥ ያስተጋባል።


<አንተ ሰው ምን አድርጊ ነው የምትለኝ?>





የ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

04 Dec, 13:10


Life doesn't deserve the amount of worry we give it . እንዲሉ አበው ጭንቀታችንን አደብ እናሲዘዋለን ።የቀረን ግዜ ብዙ እንዳልሆነ ገብቶናል !

ስንወድ አንሰስትም እራሳችን እንከን አልባ አደርገን አንቆጥርም ስናጠፋ ሸብረክ እንላለን ።

በምንወዳቸው ሰዎች ቀልድ አናውቅም ። የኛ ቀን ዛሬ እንደሆነች ዘውተር ላለመርሳት እንምክራለን ። ስንወድቅ ሃዘን አናበዛም ዘጠነኛ ክፍል ሆነን ሳይቀር የሰማናትን ቀልድ አስታውሰን ፈገግ እንላለን ።

መኖር ጥሩ ነው




Adhanom Mitku 🙌

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Dec, 15:45


Check our Sunday edition out this morning in #AddisAbeba, #Ethiopia and available online at https://addisfortune.news

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Dec, 15:45


France and Ethiopia have reinforced their bilateral relationship with a landmark agreement signed on Saturday, November 30, 2024, increasing access to education and preserving cultural heritage.

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Dec, 15:45


#FireSafety Addis Abeba is reviewing its fire safety protocols, with the Fire & Disaster Risk Management Commission introducing stringent regulations to reduce fire incidents by 70pc. With city officials addressing the pressing issue of rampant fires that have plagued Addis Abeba, the initiative particularly holds implications for commercial establishments.

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Dec, 15:45


#CBEBoardRevamp Brook Taye (PhD), the CEO of Ethiopian Investment Holdings (EIH), appointed Henok Teferra, Mahlet Kassa, and Henok Assefa to the board of the state-owned Commercial Bank of Ethiopia (CBE). They'll join a 10-member team, bringing insights and a broad range of experience from sectors like aviation, law, and entrepreneurship.

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

02 Dec, 21:07


Some Quotes 😍

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

21 Nov, 09:40


Stay Ahead in Ethiopian Business News

"Get real-time updates on Ethiopia’s economy, currency, and business trends! Dive into exclusive insights and stay informed on key issues impacting Ethiopia. Follow Addis Fortune for daily updates!"

👉 https://t.me/addisfortune

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

20 Nov, 10:20


Malaria, a persistent threat in rural areas, is resurging with alarming intensity in 2024, exposing deep-rooted systemic issues aggravated by climate change and inadequate health infrastructure. In the past three months alone, the Ministry of Health has reported nearly 2.9 million cases, a staggering 200pc increase compared to the same period in previous years.

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

19 Nov, 12:16


ለንባብ የበቁ አዳዲስ መጻሕፍት !

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

18 Nov, 14:11


"በተቀመጥኩበት ደና አልነበርኩም ወይ ?"

በተቀመጥኩበት ወትወትህ ወትውትህ ፣ ከለመድኩህ በኃላ ፣ እቅዴ ውስጥ ከከተትኩ በኋላ ፣የኔ ነው ብዬ ካወጅኩ በኃላ ...

ድሮ ባገኘሁት ኖሮ ቁጭት ከወዘወዘኝ በኃላ ፣ ደስታ እሚያደርገኝን ካሳጣኝ በኃላ ፣ ጓደኛቼው ስለራሳቸው ሲያወሩኝ እኔም ብዬ ስላንተ ማውራት ከጀመርኩ በኃላ ....

ለናፍቆቴ ፊት ከሰጠሁት በኃላ ፣ መውደዴን ያለስስት ከወረወርኩ በኃላ ፣ ጓደኛዬም ካደረኩህ በኃላ ...

"የማያቁት አገር አይናፍቅም "

መወደድን ከአየሁ በኃላ ፣ ናፍቆቴን ካስተናገድኩት በኃላ ፣ አለሁልሽ ካልከኝ በኃላ ፣ መኖርክን ከለመድኩ በኃላ ፣ ካመንኩህ በኃላ ...

ስትሄድ .....

እምነቴ ተናደ ፣ ናፍቆቴ ድብርት ወለደ ፣ ግርግሩ በአን'ዴ ጭር አለ ..!

ናፍቆት እና ማጣት አፈረሱኝ ...

ስጋቴን ቀስ ብለህ ሸርሽረህ ሸርሽረህ ከናድከው በኃላ.... !!

" ለአፍታ አላይክም ወይ አንዴ እንደገና ?"
እንማር

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

18 Nov, 01:38


እንኳን ደህና ቀሩ
[Red-8]

ዘጠና ዘጠኙን፡ አልጋዬ ስር ትቼ
አንዳንድ የምናፍቅ፡ ከጠፉት ሉኮቼ
ሥጭር ላቆሰሉኝ፡ ሙቼ ለፃፍኳቸው
አንድ ቀን አግኝቼ፡ ዳግም ላነባቸው፡
ወደ ወደቁበት ፡ ሀገርና ቅዬ
ያተጫነብኝን፡ ብዕሬን ፈንቅዬ፡
መጣለሁ ያልኩኝ፡ ከሞት ተነስቼ
እኔም ክርስቶስ ነኝ፡ ለጠፉት ግጥሞቼ።

ቢሆንም ቢሆንም፡

አዳማ ፍራንኮ፡ ከእርጎ ቤቱ በቀኝ
ይመጣል እያለች፡ የምትጠብቀኝ
ያቺ ወረቀት ግን ፡ ግጥም የፃፍኩባት
እንኳን ጠፍታኝ ቀረች፡ እንኳን ቀረሁባት።

ያቺ ኮብላይ ግጥሜ፡
መነሀሪያ አጠገብ፡ ቅጥቅጡ እስኪሞላ
ፍቅሩን በመጠበቅ፡ ለፈረሰ ገላ
ለማይረካ ናፍቆት፡ ለማይቆረጥ ጥም
ሻንጣዬን አዝዬ፡ በውሃ ጥም ዝዬ፡ የደረስኳት ግጥም
ሲበቃኝ ከኪሴ፡ አጥፌ ያኖርኳት
እንኳን የወደቀች፡ እንኳንም የጣልኳት።

አንዴ በፃፈው ልክ፡ እየተሰፈረ፡
ላንዴ ባፈለቀው፡ ጥቅስ እየታሰረ
ስንቱ ፈጣሪ ነው፡ ባለበት የቀረ?
ፍጡር ተነቦ ነው ፡ አምላኩ ሚከበር ፡
ፍጡር ተነቦ ነው፡ አምላኩ ሚቀበር
እንኳንም ወደቀች...
ብትኖር እሷን ብዬ፡ እዚያው እቀር ነበር።

አፈር ልሆን ሄድኩኝ፡ እሷን ከአፈር ጥዬ
በዝናብ ርሳ፡ በጣይ ተቃጥዬ
ያስተዋወቀንን፡ መልካችንን ትተን
ተላልፈን ይሆናል፡ ይሄኔ ተያይተን።

በተፃፃፍንበት፡ በነበር መች ቆየን?
በየደረስንበት፡ እንዳዲስ ተቃኘን
እሷ በሷ ሆዬ፡ እኔ በትዝታ
ከንግዲህ በኋላ፡ ባገኛትም እንኳ ፡ ከጣልኩበት ቦታ
አትሆነኝም ሎሌ ፡ አልሆናትም ጌታ።

እሷም ብቻ አይደለች፡ ያኮራችኝ ጠፍታ...

ከሶስት ቁጥር ቶታል ፡ በታቦት ማደሪያ
ለፀሀይ ዩኒፎርም ፡ ጋርደን ሰደርያ
ሲመሽ ከገብርኤል፡ እስከ አቦ ማዞሪያ
መንገዳችን እንጂ፡ ወሬያችን ሳይበቃን
መካኒሳን አልፈን ፡ ሳርቤት በቫቲካን
ለሚያረማምዱኝ፡ ለወክ አጣጮቼ
የታጠፈች ግጥሜን፡ ከኬሴ አውጥቼ
ቆም ሄድ እያልን፡ የመንገድ ባውዛው፡ በየደመቀበት
ያነበብኩላቸው ፡ የላመች ወረቀት...
ያቺ የዋህ ግጥም፡ «አንድም ሰው እንዳይሞት!» የሚል መዝጊያ ያላት
እንኳን የትም ጠፋች፡ እንኳን የትም ጣልኳት!

« አንድም ሰው እንዳይሞት? »
አረ ባክሽ?... እውነት?
የልጅነት ግጥሜ፡ ስሚኝ ተረት ተረት...

ዮኒፎርም አውልቀው፡ ከአብሮ አደግ ርቀው
በዓለም ስቃይ ልክ፡ ልብን አተልቀው
ከምኞት ደመና፡ በግፍ ወንጭፍ ወርደው
በወክ ካካለሉት ፡ካደጉበት ሰፈር፡ ተነቅለው ተሰደው
ተቃጥለው ከፃፉት ፡ በሀቅ በፍትሕ ጥም
«አንድም ሰው እንዳይተርፍ!» ይማፀናል ግጥም።

እንኳን ጠፋታ ቀረች፡ ግጥሜ እንደልጅነት
ዓለሙን ሳታውቀው ፡ የተፃፈች ጀነት
በምኞት ቡርሿ፡ ሲዖል ለማቆንጀት
ስትጣጣር ያኔ፡ እንኳን ነቃሁባት፡
እንኳን የትም ጣልኳት፡ ይቺ ተረት ተረት...
የወተት ግጥሞቼ፡ እየተነቀሉ፡ ሲበቅል የስጋው
ለነከሰኝ ሁሉ፡ ሰው ብዬ ስጠጋው
እንኳንስ ልታገል፡ ስለት እንዳይወጋው...
ሞት አንሷል ብዬ ነው፡ አሁን የምሰጋው።

ምን ያቺ ብቻ...?

እየደረሳቸው፡ የመሰወር እጣ
ከሀይስኩል መድረክ፡ ፑሽኪን እስክመጣ
ከአዳማ ክበብ፡ ከግቢ እስክወጣ
ከጦቢያ በጃዝ ፡ከፒክኒክ በረንዳ
ጆሮ እየጠመድኩኝ፡ በስንኝ ልነዳ
ከኪሴ እየሳብኩኝ፡ መመለስ ዘንግቼ
የትም የጣልኳቸው ፡ ባይተዋር ግጥሞቼ

ያጡትን ለማግኘት፡ ጠፍቶ ከመመኘት
ተነፋፍቆ ኖሮ፡ ተጣባብቆ መቅረት
ከሚባል መንትያ ፡ቀንበር ነፃ ይውጡ
ከእንግዲህ ግጥሞቼ ፡ ወደኔ እንዳይመጡ...

'ጠፍተን ያልተገኘን፡ ልጆችም ነን' ቢሉ
እንድውጣጣባቸው፡ ለተደለደሉ
ሆኜ ለተውኳቸው፡ ሆኜ ላለፍኳቸው፡ አልቀው ለተጣሉ
ላለፉት እኔዎች፡ መቃብሮች ናቸው፡ የፃፍኳቸው ሁሉ።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

15 Nov, 13:18


😍ፍቅር- ፈራን:ጠላን😍

"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን መቀራረብ ፈራን
እንዳልተዛመድን እንዳልተዋለድን
ፈርተን መዋደድን ጉርብትናን ናድን
እኛነትን ትተን እኔነትን ለመድን
"ፈራን"
ፍቅርን ፈራን ጥላቻን ሰራን ብቸኝነት ጠራን
በጋራ ቤታችን አጥር ድንበር ሰራን
"ናቅን"
በልዩነት ደምቀን ያልኖርን ያህል አንድም ቀን
እልህ ተናነቅን
"ናቅን"
መቻቻልን ናቅን ለፀብ አሟሟቅን
ለአመፅ ስንነሳ ለሰላም ወደቅን
አገር ስትቃጠል ከዳር ሆነን ሞቅን
"ጠላን"
መወያየት ጠላን መነጋገር ጠላን
መደማመጥ ጠፍቶ መነቋቆር በዝቶ
መናናቅ በርክቶ
መመካከርን ስንረሳ መከባበርን ስንረሳ
እጃችን በወንድማችን ላይ ዱላ አነሳ
የቃየል ምቀኝነት በልባችን ላይ ነግሳ
"ራቅን"
የተስፋ ሻማችን ተለኩሶ
ወጋገኑ መታየት ሲጀምር አድማሱን ጥሶ
እኛ ግን ራቅን ብሩህ ነገን ራቅን
ዛሬን ተጣበቅን ትላንትን ናፈቅን

ሌሬት ፀጋዬ ገ/መድህን


ሐሽማል ቤተ-መዘክር

14 Nov, 15:56


እፈራለሁ
[ ]

ቆይ፥
መንፈስ ብትሆኚስ?
ለእኔ ብቻ የሚታይ ፥ ከህልም የተሰራ፥
'ዴልዩዥን' ብትሆኚስ?
የምኞት መዶሻ ፥ ጠራርቦ ያቆመሽ ፥ የልቤ ፈጠራ፤

ከጨዋታ መሐል ፥ ድንገት ብትጠፊብኝ፤
'የታለች?' ስላቸው፥
'ማን ናት ደሞ?' ብለው ፥ ሰዎች ቢስቁብኝ፤

ህልም ብትሆኚስ?
ስነቃ ብትቀሪስ?
ቆይ አሁን፥
ጭራሹን ባትኖሪስ?

ሞልተሽኝ በእቅፌ፥
እጆቼን ቀንፌ፥
ደስታዬ እንደድመት ፥ ልቤን እየላሰው፥
ሳቅ ሆዴን ሲያምሰው፥
ባዶዬን ቢሆንስ፥
ብቻዬን እንደእብድ ፥ የምታየው ለሰው?
እንደንፋስ ነክቶኝ ፥ ሲያልፍ ሰቀቀኔ፥
ከተዳከምሁበት ፥ ከውብ ሰመመኔ፥
'ቢሆንስ?' እያልሁኝ፥
ድንገት እየባነንሁ ፥ እፈራለሁ እኔ፥

መቼም፥
ነፍሱን መርጦ አጥቦ ፥ ውድ አካል ቢያለብሰው፥
ምን ያህል ቢወደድ ፥ ፍቅር ቢያንተርሰው፥
እንዲህ ሁሉ አምሮለት
በስጋና በደም ፥ አይገለጥም ሰው።

©ሚካኤል ሚናስ

@wegochi

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

13 Nov, 15:21


ለካስ ሰው መሆን እዳ ነው
ለካስ ሰውነት ባዳ ነው
እህል ውሃ ቢያደነድነው
ሲያጣ ሲነጣ በድን ነው፡፡
የኛስ ይሁን እንዳሻው ለእጥፍ ፈተና ከፈጠርከን
ለፍታችሁ ተፍታችሁ ኑ ካልከን
ለቀብር አፈር ከወጠንከን
ግን ፡- ግን ብላቴኖች ምን በደሉ
የማንን አደራ በልተው የማነን አማና አጎደሉ
እንብርታቸው ያላረረ
አጥንታቸው ያልከረረ
ሰማይ በቀል እንደቋጠረ
እጣቸውን እየመጠረ
መንገዳቸውን በእሾህ እያጠረ
እንደ ደራሽ ውሃ አግተልትሎ
በራብ አኮርማጅ ተልትሎ
ከእናት እቅፍ በግፍ ነጥቆ
ሲሰልፍብን ባጭር ታጥቆ
እያየህ ዝም ካልክማ
እውነት እውነት ከመንበርህ የለህማ!

[አያ ሙሌ ]

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

12 Nov, 14:16


መንገድ ጠፍቶን ስንደናበር ላረጋጉን ፣ ወደቅን ስንላቸው ላልፈረዱብን ። በድለናቸው ይቅርታን ለሰጡን ፦

ሚስጥራቸውን ላጋሩን፣ ደስታችን ለተካፈሉ፣ ሃዘናችንን ቦታ ለሰጡት ፣ ለተጠነቀቁልን ፣አጋርነታቸው ወረት ለሌለበት ፣ በቆሚነት የኛ ለሆኑ ።

እንድናምናቸው ለሆኑ ፣ ደግነታቸው ለማይስተን ፣ ለሚወዱን ፣ ሊረዱን ግማሽ መንገድ ለሚመጡ ፣ ለሚያበረቱን

ችርስ ለነሱ 🙏

ኑሩልን

©Adhanom Mitiku

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

11 Nov, 10:07


የሚገርሙኝ ዘመን ተሻጋሪ ቃላት - ከእመጓ መፅሐፍ
________

- በዓለማየሁ ዋሴ እሸቴ (ዶ/ር)
(ገፅ 162-163)

በአፍላ ትጀምራላችሁ በወረት ትተዉታላችሁ፡፡ ያወቃችሁትን ትረሳላችሁ፤ ያላወቃችሁትን ለማወቅ ትጥራላችሁ፤ የያዛችሁትን ትረግጣላችሁ፤ የረገጣችሁትን ትይዛላችሁ፡፡ ምኞታችሁ ልክ የለውም፤ አምሮታችሁ ብዙ ነው፡፡

የአማራችሁን ስታገኙ ወዲያው ይሰለቻችኋል፡፡ ተዉ የተባላችሁትን ትሽራላችሁ፤ የተከለከላችሁትን ትደፍራላችሁ፤ የተፈቀደላችሁን ችላ ትሉታላችሁ፡፡ …

ሁሉን ማወቅ ትፈልጋላችሁ፤ በአንዱም ግን አትጠቀሙበትም፡፡ ሁሉ አላችሁ፤ ግን ባዷችሁን ናችሁ፡፡ ሃይማኖት እንጅ እምነት የላችሁም! …

መቀመሚያውን ነግሬህ ማርከሻውን ሳልገልጥልህ መጀመሪያውን ብቻ ሞጭልፈህ ትተኸኝ ትሄዳለህ፡፡ ጥበብን ‹‹ሀ ግዕዝ›› ብዬ ላስተምርህ ብሞክር፣ መንደር ውስጥ በቃረምካት ዕውቀት ተመክተህ በመሰልቸት ‹‹ሆ ሳብዕ›› ብለህ ቀድመህ ትዘጋዋለህ፡፡

የግል ታሪካችሁ ቢታይ ወጥነት የጎደለው ከዚህም ከዚያም የተልከፈከፈ የተማሪ ኮፋዳ ውስጥ ያለ እህል ይመስላል፡፡

ተምራችሁ እውቀት ስታገኙ፣ ሰርታችሁ ሀብት ስታፈሩ፣ ከላይ የሆናችሁበትን ሃገር ለቃችሁ፣ ሰፋ ወዳለው እንሂድ ብላችሁ እንደገና ከታች ትጀምራላችሁ፡፡ ትቀጥላላችሁ፣ በመጨረሻ ከጀመራችሁበት ትገኛላችሁ፡፡ ቸኩላችሁ ትወስናላችሁ ወዲያው ትጸጸታላችሁ፡፡ በጽኑ ታማችኋል!

ከታሪክ ፍቅርንና ልማትን ሳይሆን ጥላቻንና ጥፋትን ለይታችሁ ትቆፍራላችሁ፡፡ ከዚያም ቀጥላችሁ የከበረ ማዕድን እንዳወጣችሁ ሁሉ በኩራት ደረታችሁን ነፍታችሁ ሳትመርጡ ሁሉን በአደባባይ ትዘሩታላችሁ፤ እናም ወደ ኋላ ስለታሪካችሁና ስለ ቅርሳችሁ ባሰባችሁ ቁጥር ፍርሃትና ሃፍረት ይሰማችኋል፡፡

ስለሆነም ከኋላ ታሪካችሁና ክብራችሁ እየራቃችሁ መጣችሁ። የአሸናፊነትንና የተሸናፊነትን ትርጉም በአንድ ላይ የያዙ ሃውልቶች ታቆማላችሁ፡፡ ለግልጽነትና ለነጻነት እያላችሁ በምታደርጉት ሽኩቻ ዕርቃን ወደ መሆን ወረዳችሁ፡፡

ቅቤ ላይወጣችሁ ትናጣላችሁ፡፡ በዚህ ዓለም ጥድፊያ ታማችኋል፡፡ ሀገራችሁን ትንቃላችሁ፤ ጥላችሁ ለመሄድ ትፈልጋላችሁ፤ ከሄዳችሁ በኋላ ደግሞ አፍታ ሳትቆዩ አገሬ ናፈቀኝ ትላላችሁ፡፡

በቁማችሁ የናቃችሁትን የሀገራችሁን አፈር በሞታችሁ ልትለብሱት ትናፍቃላችሁ፡፡ ለሀገሬ አፈር አብቃኝ ብላችሁ በድናችሁን ልካችሁ የወገኖቻችሁን ልብ ትሰብራላችሁ፡፡

ግብዝነታችሁ መጠን የለውም፡፡ ሁለት ሀገር እንዲኖራችሁ ትፈልጋላችሁ፤ አንዱን በደም ሌላኛውን በመታወቂያ ታስባላችሁ፡፡ ከአንዱም ግን በአግባቡ አትኖሩም፡፡ ዘመናችሁም በምልልስና በመዋተት ያልቃል፡፡

ምን እንደምትፈልጉ አታውቁም እናም ፍለጋችሁ አያልቅም፡፡

ፈጣሪ የልጆቿን ልቦና ወደ ተቀደሰው ሥፍራ ይመልስ!

ኢትዮጵያችንን አብዝቶ ይባርክ!

ለደራሲው ከከበረ ምስጋና ጋር፣

መልካም ጊዜ!

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

10 Nov, 17:00


ሰዎች ደስተኛ ከሆኑ የህብረተሰቡ ጠቅላላ ቅርፅም ይቀየራል።

(ኦሾ)

" 'የምንኖረው ምን አይነት ማህበረሰብ ውስጥ ነው?' ብዬ ጠየቁ።እኛ ማህበረሰብ ውስጥ ሰው ሲሰቃይ ሁሉም ነገር መልካም እንደሆነ ይታሰባል።አንድ ሰው ሲፈነድቅ ስናይ እብድ እንደሆነ እናስባለን።ህብረተሰቡ ደስታን አይፈቅድም።እየተሰቃያችሁ ከሆነ ማንም ሰው አብደዋል ብሎ አያስብም።መፈንደቅ፣መሳቅ ስታስቡ ግን ሁሉም ሰው እብድ እንደሆናችሁ ያስባል።

ደስተኛ ሰው ስናይ አንድ የሆነ ችግር እንዳለበት እናስባለን።ነገር ግን ስቃይ ኢ-ተፈጥሯዊ ነው።ሰዎች ደስተኛ እንዲሆኑ መላው ህብረተሰብ መለወጥ አለበት፤ምክንያቱም ይህ ማህበረሰብ በስቃይ ውስጥ ያለነውና?? ሰዎች ደስተኛ ከሆኑ የህብረተሰቡ ጠቅላላ ቅርፅም ይቀየራል።"

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

10 Nov, 08:43


አሌክሳንደር ፑሽኪን
(1799_1837 )
በ 1799 ተወለደ በጊዜው ተራማጅ አስተሳሰብ የነበረው ፑሽኪን ህይወቱን ለሩሲያ ሥነጽሑፍ እድገት ያዋለ በመሆኑ የሀገሪቱ የመጀመሪያ የፈጠራ ጽሑፍ ጠቢብ ለመባል በቅቷል የፑሽኪን የሥነጽሑፍ ውጤቶች የምዕራባውያን ባለቅኔዎችና የብዕር ሰዎች ተጽዕኖ የዳሰሳቸው ቢሆንም አርአያና ምሳሌ ለመሆን በበቁት በቅኔው በተውኔቱ በልቦናና በአጫጭር ድርሰቶቹ ጥልቀትና ምጥቀት ብሔራዊ ባለቅኔነቱን ለማስመስከር ችሏል ፑሽኪን በሰፊ የሥነግጥም የስድ ጽሑፍ አዝመራው አማካኝነት ዘመናዊውን ሥነጽሑፍ ቋንቋ ለሩሲያ ያበረከተ ታላቅ የፈጠራ ሰው በመሆኑ " የሩሲያ ሥነጽሑፍ ታላቁ ዼጥሮስ" እያሉ የሚጠሩት አልታጡም የቀድሞዋ ሶቬት ህብረት የዛሬዋ ሩሲያ የሕዝባችን ነፍስ የሚል ስያሜ የሰጡት ያለምክንያት አይደለም የአርበኝነት ባሕሪ ጠንካራ ብሔራዊ ኩራት ለሩሲያ አፈር ያለውን ጥልቅ ፍቅር ከአብዮታዊ ስሜቶች ጋር በማዋሐድ በቅኔዎቹ ይገልጥ ስለነበር ነው።
ይህም ስለ ስራውና ስለ ህይወቱ በሚተርከው ገድሎቹ ውስጥ ተመዝግቧል በተለይም በከፍተኛ ስሜት ይደግፈው በነበረው የታሕሳሳዊያን ንቅናቄ እየተባለ በሚጠራው በ1828 እንቅስቃሴ ውስጥ ተጋድሎ ላደረጉት አርበኞች ጓደኞቹ መታሰቢያ የጻፋቸው ቅኔዎች ለዚህ ቋሚ ምስክር ናቸው ።
ፑሽኪን ኢትዮጵያዊ ደም ነበረው በሀገራችን በይበልጥ የሚታወቀው በኢትዮጵያዊው ቅድመ አያቱ በአብርሃም ሐኒባል ታሪክ እንጂ እንብዛም በኪነታዊ ሥራዎች አይደለም ወደ አማርኛ ከተመለሱት ጥቂት አጫጭር ታሪኮቹ በስተቀር ዋነኞቹ የፑሽኪን የጥበብ ውጤቶች በተለይም ድንቅ ቅኔዎቹ እስከዛሬ ልሳናት አልተተረጎሙም ።
ፑሽኪን ከሥራዎቹ መካከል የሚበረከቱትን ያቀረበው በሥነ ግጥምና በአጫጭር ድርሰት ቅርጽ ሲሆን "አሮጊቷ " በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ የተተረጎመው ተወዳጅ ሆኖለታል ልዩ ተሰጦዖ የነበረው የዚህን ታላቅ ከያኒ ሥራዎች በተለይም ቅኔዎቹን በርካታ ምሁራንና የሥነጽሑፍ አፍቃሪዎች ዛሬ በመላው ዓለም እንደሚያስተጋባቸው ሁሉ ይህ አጭር ድርሰቱም በመላው ዓለም በልዩ ልዩ ቋንቋዎች ከመተርጎሙም ሌላ በተንቀሳቃሽ ፊልም ተቀርፆ በመታየት ሁለንተናዊ አድናቆት ያተረፈ ነው ።
የፑሽኪን መጨረሻ ድንገታዊና የሚያሳዝንም ነበር በአንዳንድ ምክንያቶች የተነሳ ዳንቴስ በሚባል ሰው ጋር የከረረ አለመግባባት ይፈጠርና ሁለቱ ጠበኞች በተኩስ ለመፋለም ይወስናሉ እኒሁ ግለሰቦች የካቲት ስምንት ቀን 1837 ባደረጉት የተኩስ ፍልሚያ የሠላሳ ሥምንት ዓመቱ ጎልማሳ በለጋነቱ ተቀጨ ።
መስፍን ዓለማየሁ እንደፃፈው

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

09 Nov, 09:43


What is life?
• Dostoevsky: It’s hell.
• Socrates: It’s a test.
• Aristotle: It’s the mind.
• Nietzsche: It’s power.
• Freud: It’s death.
• Marx: It’s the idea.
• Picasso: It’s art.
• Gandhi: It’s love.
• Schopenhauer: It’s suffering.
• Bertrand Russell: It’s competition.
• Steve Jobs: It’s faith.
• Einstein: It’s knowledge.
• Stephen Hawking: It’s hope.
• Kafka: It’s just the beginning.

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

08 Nov, 07:55


⭐️

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

08 Nov, 07:53


የትርክት ዕዳና በረከት
ዳንኤል ክብረት

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

07 Nov, 13:35


Stay Ahead in Ethiopian Business News

"Get real-time updates on Ethiopia’s economy, currency, and business trends! Dive into exclusive insights and stay informed on key issues impacting Ethiopia. Follow Addis Fortune for daily updates!"

👉 https://t.me/addisfortune

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

07 Nov, 11:42


ምክንያቱ ምንም ይሁን የደከማችሁ ከምር አይዟችሁ። በተለይ ወጣት ሆናችሁ የደከማችሁ አይዟችሁ። በምድር ላይ ከባዱ ስራ ፣ መስራት እየቻሉ ምንም መስራት አለመቻል ይመስለኛል ። ከስጋ አልፎ ነፍስን ነው የሚያደክመው። ምንም ይሁን ግን አይዟችሁ። አይዞን!

አሌክስ አብርሃም

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

06 Nov, 13:40


#ፍቅር_ማለት?
#አንተን_ትክክል_ለማድረግ_የምሮጥበት_መስኬ_ነው።

ዘወትር ከሰዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ሀሳቦቻችንን ሲያፀድቁልን ትክክል ስለሆንን ነው ብዬ አስብ ነበር።

#ባርች ካፍቴሪያ ቀጥራኝ ትንሽ ስላረፈደችብኝ ስልኬ ላይ ከያዝኳቸው መፅሀፎች መሀል የአሌክስ አብርሀምን ከዕለታት ግማሽ ቀንን መሀል ላይ ከፍቼ እያነበብኩ እያለ።

"ትንሽ ዘገየው አይደል? መንገዱ ተዘጋግቶ ነው ኮ" ብላኝ ከፊት ለፊቴ ያለውን ወንበር ስባ ቁጭ አለች።

አይ ባርች ሁሌም የሚገርመኝ ይሄ ባህሪዋ ነው ላጠፋችው ፣ ላደረገችው,,,ወዘተ ነገሮች ሁሉ ሰዎች ሳይጠይቋት ምክንያቷን ማቅረብ የዘወትር ተግባሯ ነው።

ያዘዘችው ማኪያቶ እስኪመጣላት በመሀል "አየሽ በዛ ጉዳይ እኔ ትክክል ሆንኩ አይደል"? አልኳት

ያንን ጉንጮቿን ብቻ ግራና ቀኝ ሳብ አድርጋ ጥርሷ ሳይታይ ፈገግ የምትለውን ፈገግታ ከጋበዘችኝ በኋላ "ትክክል እኮ ሆነህ አይደለም " አለችኝ።

እኔም "እንዴ ይሄ ደሞ ምን ማለት ነው?" አልኳት።

"እየውልህ #ኻህሊል_ጂብራን ከፍቅረኛው ጋር ሰባት አመት ሙሉ በደብዳቤ ብቻ ሲያወሩ ከቆዩ በኋላ አንድ ቀን እስቲ ፎቶሽን ላኪልኝ? አላት"

እኔም "ከዛስ?" አልኳት

"ከዛማ እሷ ፎቶዋን ከመላኳ በፊት እንዲህ አለችው "እስቲ በምናብህ ሳለኝ፣ ገምተኝ ምን አይነት ሴት እመስላለሁ"? ብላ ጠየቀችው።

#ኻህሊልም "ፀጉሮቿ አጫጭር የሆነች ሴት ትመስሊኛለሽ" አላት

#እሷም "ፀጉሯን በአጭሩ ተቆርጣ ፎቶ ተነስታ ላከችለት" ከዛ, ,ብላ ወደ ሌላው አረፍተ ነገር ሳትሄድ

"እና ታዲያ ይሄ ከኔ #ትክክል ነኝ ካልኩት ሀሳብ ጋር ምን አገናኘው"? አልኳት

#ባርችም ስክነት በውስጣቸው በሚያስተጋቡ ቃላት "እስቲ ተረጋጋና ታሪኩን ልጨርስልህ" አለችኝ

#እኔም ይሄን ታሪክ ከኔ ሀሳብ ጋር እንዴት እንዳገናኘችው ባይገባኝም ታሪኩን ግን መጨረሻው ስላጓጓኝ "እሺ ጨርሺና እንስማው እስቲ" ብያት የቀረበልኝን ማኪያቶ አንዴ ፉት አልኩት።

#ባርችም ቀጠል አድርጋ "#ኻህሊል_ጂብራንም የዛን ወቅት ነበር ፍቅረኛውን "አየሽ እኔ ትክክል ነኝ ያላት ፣ #እሷ ግን ትክክል አልነበርክም አለችው ቀጠል አድርጋም #እኔም ትክክል አይደለሁም ታውቃለህ በመሀከላችን #ትክክል የነበረው ነገር #ፍቅር ነው አለችው።"

እና ኸታቢው ምን ልልህ ፈልጌ መሰለህ በሀሳቦችህ #ስለማትሳሳት አይደለም አብሬህ ያለሁት #ፍቅር ማለት አንተን ትክክል ለማድረግ የምሮጥበት #መስኬ ስለሆነ ነው" አለችኝ።

እኔም እንዳቀረቀርኩ ብዙ የሚወዱን ሰዎች የሀሳባችን ጥንካሬና ትክክለኛነት ሳይሆን እነሱ ልብ ውስጥ ባለን ደረጃ ልክ ነበር ለካ ሀሳቦቻችንን #ትክክል በሚባል ማማ ላይ ከፍ አድርገው የሚሰቅሉልን።
አሁን በልቤ ውስጥ ለመብሰል ከጎደለኝ ግብአት ውስጥ አንደኛው ጉድለቴ ሲሞላ ታወቀኝ።
"#ባርችም በል ተነስ ዛሬማ ብቻዬን አልሄድም" ብላኝ የተጠቀምነውን ሂሳብ ከፍለን በዝምታ ጎን ለጎን ረጅም መንገድ ተጓዝን ለነገሩ ዝምታም ኮ የመብሰል ሌላኛው ግብአት አይደል።

#ኸታቢው_ዐይኔ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

06 Nov, 06:40


Stay Ahead in Ethiopian Business News

"Get real-time updates on Ethiopia’s economy, currency, and business trends! Dive into exclusive insights and stay informed on key issues impacting Ethiopia. Follow Addis Fortune for daily updates!"

👉 https://t.me/addisfortune

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

06 Nov, 02:40


ብዙ ስታወራ አብዝተው የሚያዳምጡህ ሰዎች ላንተ ምላሽና ሌላ አስተያየት ከሚሰጡህ ይልቅ መታዘብ ይቀላቸዋል! አንተ ግን ሁሉን ስታወራ ልክነትህን እያመኑልህ እንደሆነ አታስብ!!!

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

05 Nov, 09:58


𝐁𝐄𝐑𝐄𝐊𝐄𝐓 𝐁𝐀𝐋𝐂𝐇𝐀: The stakes of the upcoming U.S. election extend far beyond America’s borders, rippling across continents already destabilized by growing conflicts. This year's election arrives amid unprecedented global turmoil, where the world seems closer to the brink of catastrophe than ever before.

Read more

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

04 Nov, 12:53


According to the Ministry of Agriculture's first-quarter report, the plan was to buy and distribute 2.4 million tons of fertiliser this year, of which 1.33 million tons is DAP. Last year, two million tons were bought, with 1.65 million tons distributed. The Ministry has already dispatched 512,201tns in the first quarter.

Read more

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

04 Nov, 03:59


ሚዛናዊ የስሜት አገላለጥ

ከሰዎች ጋር ባላችሁ ግንኙነት ስሜታችሁን የሚነካ ነገር ሲያጋጥማችሁ ከሁለት ስህቶች ተጠንቀቁ፡፡

1. ስሜታችሁን እንደወረደ ከመልቀቅ መጠንቀቅ

አንድ ስሜት ሲሰማን ያንን ስሜት ካለምንም ገደብና ሚዛናዊነት እንደወረደ ስንለቀው ያልተጠበቀና ልንቆጣጠረው የማንችለው ውጤት ሊያስከትልብን ይችላል፡፡ ከእነዚህ አጉል ውጤቶች መካከል፣ ሰዎችን መጉዳት፣ ከቁጥጥር ውጪ የሆነና ነገሩን የሚያባብስ የሰዎች ምላሽ መከሰት እና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ነገሮች እየተባባሱ የኋላ ኋላ የማንፈልጋቸውንና መዘዝ የሚያመጡ ሁኔታዎችን ሊወልዱ ይችላሉ፡፡

2. ስሜታችሁን ከማፈን መጠንቀቅ

ሰዎች ስሜታዊ የሚያደርገንን ነገር ሲያደርጉብን፣ የሚሰማንን ስሜት አምቀን በያዝነው ቁጥር ከፍተኛ የሆነ ጉዳትን በራሳችን ላይ ያስከትላል፡፡ ከእነዚህ ጉዳቶች አንዱ፣ በታመቀው ስሜት ምክንያት የሚመጣ የውስጥ መጎዳት ነው፡፡ ከዚህ የተለየውና ብዙዎች የማያስተውሉት ሌላው ጉዳት፣ ስሜታችንን አምቀን ከቆየን በኋላ ሲብስን ድንገት “የመፈንዳት” ሁኔታ የሚያስከትለው መዘዝ ነው፡፡

የዚህ ሁኔታ ችግሩ፣ አምቀን የቆየነውንና ማንም ሰው የማያውቀውን ስሜት በድንገት ስንለቀው ሰዎች እስካሁን ያለፍንበትን ሁኔታ እና ያመቅነውን ስሜት ስለማያውቁት፣ እንደ አጉል ስሜታዊ ይቆጥሩንና ጥፋቱን ሁሉ በእኛ ላይ ያደርጉታል፡፡ ይህ ደግሞ ሌላ ጉዳትን ያስከትልብናል፡፡

እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ጎጂ ሁኔታዎች እንዳይከሰቱ ለማድረግ ከፈለግን ስሜታችንን ለትክክለኛው ሰው፣ በትክክለኛው ቦታ፣ በትክክለኛው ጊዜ እና በትክክለኛው መጠን መግለጥን መለማመድ አስፈላጊ ነው፡፡ ይህንን ሁኔታ የተለማመደ ሰው ከፍተኛ የስሜት ብልህነት ደረጃ ላይ ያለ ሰው ነው፡፡ ምንም እንኳን ሙሉ ለሙሉ ከስሜታዊነት ነጻ የሆነ ልምምድ ባይኖረንም በተቻለን መጠን ግን ይህንን መመሪያ መከተል ለግልም ሆነ ለማሕበራ ስኬታማነታች አስፈላጊና ወሳኝ ነው፡፡
ዶክተር ኢዮብ ማሞ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Nov, 18:26


°Real story.

ነጭናጫ ሰው አይደለኹም...ለምን እንደሆነ ባላውቅም ከአንቺ ጋር፣ከእናቴ ጋር እና እንደ አጠቃላይ እንደ ራሴ ከምወዳቸው ሰዎች ጋር ስሆን protective የመሆን ዝንባሌን አመጣለኹ።እንዲህ እንዳትሆኝብኝ እንዲያ እንዳትሆኝብኝ የሚል ሐሳብ ስለሚይዘኝ ፤ ነጭናጫ ሰው እሆናለኹ።

...ለጥያቄሽ ብዙ ትኩረት አልሰጥም...እኔን ለማዝናናት የምታደርጊውን ጥረት ችላ ብዬ ፣ ዛሬን ማጣጣም ትቼ ስለነጋችን እጨነቃለኹ።

ኋላ ላይ ከተለያየን፥አንቺም ቤትሽ እኔም ወደ ቤቴ ከሄድን በኋላ ፤ ጭንቀቱ ተራ በአዕምሮዬ የተፈጠረ ሐሳብ እንደሆነ ስረዳ በፀፀት እታመማለኹ።

ምና'ለ በቀልዶችሽ አብሬ በሳቅኹ
ምና'ለ በሙዚቃው አብሬ በደነስኹ
ምና'ለ የምትነግሪኝን ከልቤ ብሰማሽ
ምና'ለ ምና'ለ እያልኹ !
...ጭንቅላቴ የሌለ scenario እየፈጠረ እንደሚያስጨንቀኝ እረሳው እና ደግመን ስንገናኝ እንደገና ልፀፀት ፤ ዛሬን ማጣጣሙን ትቼ እጨነቃለኹ...እንጂ እኔ ነጭናጫ ሰው አይደለኹም።


Sponsored by Add'o coffee house


ከ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

02 Nov, 09:31


ቮልቴር፣ ፈረንሳዊው የእውቀት ፀሐፊ፣ ፈላስፋ እና ሳቲስት፣ የመናገር ነጻነት ሻምፒዮን እና አድሎን አጥብቆ የሚተች ነበር። የኖረው ሃይማኖታዊ ዶግማ እና የፖለቲካ ሳንሱር ግለሰባዊ መገለጫዎችን በሚጨቁንበት ጊዜ ነው። " I don't agree with what you have to say, but I will defend to death for your right to say it." የሚለው ዝነኛ ጥቅሱ ለመሠረታዊ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ያለውን የማያወላውል ቁርጠኝነት ያሳያል።

ይህ ጥቅስ የንግግር ነፃነትን አስፈላጊነት ላይ ብቻ የሚያጠነጥን ሃሳብ ብቻ አይደለም; የእውነት እና የመረዳትን ተፈጥሮ በጥልቀት የተመለከተ ጥልቅ ፍልስፍናዊ ግንዛቤ ነው። ቮልቴር ከአንድ ሰው ሀሳብ ጋር ባንስማማም እነዚያ ሃሳቦች ባናምንባቸውም ወይም የተሳሳቱ ቢሆኑም እንኳ ሃሳቦቹን ለመረዳት እና ለመመርመር የምናደርገው ሂደት ለአእምሮ እድገት ወሳኝ መሆኑን ተገንዝቧል። የሃሳብ ልውውጥ እንዲኖር በመፍቀድ እውነት የሚወጣበት፣ አመለካከቶች የሚፈተኑበት እና መግባባት የሚያብብበትን ሁኔታ እንፈጥራለን።

አንድ ድምጽ ብቻ የሚፈቀድበት፣ ያንን ድምፅ የሚቃወሙ አስተያየቶች የሚነቀፉበት፣ እና ተለምዷዊ ሁኔታን የመቃወም ነፃነት የተከለከለበትን ዓለም አስቡት። ይህ ዓለም የማወቅ ጉጉት የሌለበት፣ እድገት የታፈነበት እና የሰው መንፈስ የታሰረበት ዓለም ይሆናል። የቮልቴር ጥቅስ እውነትን መፈለግ ቀጥ ያለ መስመራዊ መንገድ ሳይሆን የተመሰቃቀለ፣ አንዳንዴ የማይመች የአሰሳ፣ የክርክር እና የሂሳዊ አስተሳሰብ ሂደት መሆኑን ያስታውሰናል።

አንድ መንደር እየሆነች ባለች ዓለም፣ ኢንተርኔት የምክንያታዊ ሃሳብንም የጭፍን ጥላቻ ድምጾችንም በሚያጎላበት ዘመን፣ የቮልቴር ቃላት ከመቼውም ጊዜ ይበልጥ ጠቃሚ ናቸው። ሃሳባችንን የመናገር መብታችን፣ ለራሳችን ብቻ ሳይሆን ለመላው ሰው አጥብቆ ሊጠበቅ የሚገባው መብት ነው፣ ምክንያቱም ያለመስማማት፣ የመነታረክ እና የመሞገት ነፃነት ላይ ነው እውነተኛውን የእውቀት መንገድ የምናገኘው።

✍️ ዮናታን በጋሻው (ቀዳማዊ)

#ፍልስፍና #የህይወት #ጥልቅ #ጥበብ #መብት #ነፃ #ሃሳብ #ቮልቴር

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

01 Nov, 18:22


ልስን ድሃ
(አሌክስ አብርሃም)

የዛሬን አያድርገውና "ያጣ የነጣ" የሚለው አባባል ድሃና ድህነትን የሚገልፅ አባባል ነበር። አሁን ላይ በተለይ የከተማ ድሃ ያጣል ግን አይነጣም። ከምግብ ሳይሆን ከሜካፕ እና ከፊልተር በሚፍለቀለቅ ወዝና ውበት በአካልም በሚዲያም እያማረ ይራባል። ድሃ ነው ግን አይነጣም ፣አይገረጣም። ሜካፑና ገፅታው እንዳይበላሽ የሚያለቅሰው ወደውስጡ ነው። ይህ ውበት የነጣና ያገጠጠ ድህነትን ከላይ በሚያብረቀርቅ ነገር በመለሰን የሚሸፋፍን ሲበዛ አሳሳች ውበት ነው። አንዳንዴ ባለቤቱን ራሱን ጭምር ይሸውዳል።

ልክ እንደመቃብር ሃውልት የውጩ ውበት የውስጡን አፅም ይሸፍንብናል። በዛ ላይ ሀውልቱ ላይ የሚፃፈው የተጋነነ ታሪክና የሚለጠፈው ፎቶ ለሟች ከማዘን ይልቅ በሀውልቱ እንድንደመም ያደርገናል። የሟች ቤተሰቦች ከሟቹም በላይ አንጀታቸውን አስረው ለሀውልት ባወጡት ወጭ ያለቅሳሉ። መፅሐፉ "እናተ በኖራ የተለሰናችሁ መቃብሮች ናችሁ" ያለውኮ እንዲህ ያለው የውስጥና የውጭ ባህሪ አልገጥም ቢለው ነው። ነገሩ ግለሰባዊ ብቻ አይደለም ከተሞችም ተመሳሳይ ባህሪ አላቸው። ለምሳሌ አዲስ አበባን ተመልከቱ። በመብራት፣ በቀለም፣ በህንፃ ተለስና ስትታይ ከምድራችን የድሃ ድሃ አገራት የአስከፊዋ ድሃ አገር ዋና ከተማ ትመስላለች? የድሀ ድሀ ፣ ልዝብ ደሃ፣ መራር ደሃ ከሚሉት ማዕረጎቻችን በተጨማሪ " ልስን ድሃ" የሚል የድህነት ደረጃ ጨምረናል።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

01 Nov, 05:36


📚ርዕስ - አልተዘዋወረችም
📝ደራሲ - አሌክስ አብርሃም
📜ይዘት - ልቦለድ
📆ዓ.ም - 2016
📖የገፅ ብዛት - 239
📌አዘጋጅ - ማኅሌታይ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

31 Oct, 11:22


እማማ አፀደ የሚባሉ ጎረቤት አሉን የእናቴ ጓደኛ ናቸው። እማማ አፀደ አመም አድርጓቸው ህመማቸው በባሰ ቁጥር እናቴን ጠሏት።

ይሰድቧታል ሌባ ናት ይላሉ።
መሰሪ ናት ይላሉ።
ልትገለኝ ትፈልጋለች ይላሉ።
መርዝ አበላቺኝ ይላሉ ። አትምጣብኝ ብለው ስሞታ ይናገራሉ ሌሊት እቤቴ ልትገባ ነበር ይላሉ ።

ሰው እንዳትመስላችሁ ይላሉ ። እናቴ ቤታቸው መሄድ አቆመች ።

ከቤት መውጣት እያቆሙ ግቢያቸው መዋል ጀመሩ ....

እናቴ እሷ መሆኗን አትንገሩ ብላ ፤ ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸውን ልጅ ፤ ምን ጎደለ ጤናቸው እንዴት ነው እያለች ትሰልላቸዋለች...

ንዴት ሊገድለኝ ይደርሳል ። እቆጣታለሁ << ስምሽን እያጠፉሽ እየሰደቡሽ እየጠሉሽ አትተያቸውም ወይ?>> እላታለሁ!!

<<ጭንቅላታቸው እጢ ወጥቶባቸዋል እሱ ነው ትንሽ ቀየር ያደረጋቸው እንጂ ፤ እሳቸው እንኳን ሳልበድል ብበድላቸው እንኳን በክፉ አያነሱኝም>> ትለኛለች።

ምግብ ትልክላቸዋለች ። በእህታቸው ልጅ በኩል የሚያስፈልጋቸውን መድኃኒት መግዣ ከኛ ወስዳ ... ተበድራም ቢሆን ትገዛላቸዋለች ። እሳቸው ያቺ ምናምንቴ ፣ ድግምታም ያቺ ነጠላ እያሉ ጮክ ብለው እናቴን ሲሰድቧት ይውላሉ ።

ጠላኋቸው !!

አንድ ቀን ለምን ግን እንዲ ስምሽን እያጠፉ እየጠሉሽ እያልፈለጉሽ አልጠላሻቸውም? ብዬ እናቴን ጠየቅኋት።

<<ጓደኛዬ ናቸው! እዚህ ሰፈር ስመጣ እሳቸው ናቸው ያለመዱኝ ። እድር ያስገቡኝ ፥ የሌለኝን እቃ ያዋሱኝ ፥ የተቆረቆሩልኝ ፥ የአረሱኝ ፣የመከሩኝ...

እንዲህ አይባልም እያሉ መንገድ ያሳዩኝ እርሳቸው ናቸው ። ድንገት ታመው ነው የተቀየሩት ።ከሁሉም ጋር ነው መጣላት የጀመሩት እኔ ላይ ትንሽ ጠንከር አሉ እንጂ ...

በክፉ ግዜ እንኳን ወዳጅ ላይ ጠላት ላይ አይጨከንም!!

የጨዋ ሰው ልክ የሚታየው ሲጣሉት ነው ። በፍቅር ግዜ ሰው አይመዘንም ክፉ ግዜ ነው ሰው የሚያጠለው ....

አፀዱ እንዴት አይነት ጥሩ ሰው መሰሉህ ዛሬ ህመም ተጣብቷቸው እን'ጂ ። ስንት ቀን መሰለህ እጦት በሳቸው ሳብያ ከቤታችን የተባረረው ።
አፀደ ደግ 'ሩህሩህ ናቸው...

እናንተ ሳትወለዱ ማንም ሳይኖረኝ ነው ከኔ ጋር የነበሩት...

የአፀደ ውለታ አለብኝ !>>
© Adhanom Mitiku

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

31 Oct, 07:48


📚ርዕስ -ትቤ አክሱም መኑ አንተ
📝ደራሲ - አስረስ የኔሰው
📜ይዘት - ታሪክ
📆ዓ.ም - 1921
📖የገፅ ብዛት - 334
📌አዘጋጅ - Ytb Tse 🖤

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

30 Oct, 15:20


ያከሸፈቻቸው ያከሸፏት አገር!
(አሌክስ አብርሃም)

የ8ኛ ክፍል ተማሪወች እንደነበርን ነው። አንድ ቀን የሆነ አስተማሪ ቀረ። በዛ ክፍት ክፍለጊዜ ሁላችንም ደስ ያለንን ስንሰራ (አብዛሀኞቻችን ወሬና መንጫጫት) አንድ ምስጋናው? የሚባል ስዕል መሳል የሚችል የክፍላችን ልጅ ብላክቦርድ ላይ በወዳደቀ ቾክ ሁለት ሰወችን ሳለ። ስዕል ስላችሁ ይሄ ዝም ብሎ የልጅ ስዕል አይደለም፣ ባስታወስኩት ቁጥር የሚገርመኝ የፊታቸው መስመር፣ ፊታቸው ላይ ያረፈው ጥላ፣ ልብሳቸው ላይ ያለው ፓተርን እና ጌጣጌጥ ሳይቀር ፎቶ የሚመሳስሉ ፖርትሬቶች። ደግሞ የሳለው ምንም እያየ አልነበረም። እማሆይ ቴሬሳ ሁለት እጆቻቸውን እንደህንዶች ሰላምታ አገናኝተው ግንባራቸውን እንዳስነኩ እጃቸው መሀል መቁጠሪያ ተንጠልጥሎ፣ እንዲሁም ቀዳማዊ ሀይለስላሴ ከነንጉሳዊ ልብሳቸው ወደጎን ዞር ብለው። ሁላችንም ተገረምን ተደነቅን። የስእሎቹ መጠን የእውነት ሰው ያካክሉ ነበር።

ቀጣዮ ክላስ ጅኦግራፊ ። ኮስታራው አስተማሪያችን ገባና ስዕሎቹን አየት አድርጎ "ማነው የሳለው?" አለ ። በአንድ አፍ "ምስጋናው" አልን በአድናቆት ጭምር። ራሱ ወደምስጋናው ወንበር ተራምዶ ለአንድ ክፍል ልጅ የያዘው ልምጭ ተሰባብሮ እስከሚያልቅ ቀጠቀጠው። ምስጋናው በህመም ተንሰፈሰፈ። እና በቁጣ "ይሄ የተከበረ የትምህርት ገበታ ነው ! ማንም እየተነሳ የሚሸናበት አይደለም፤ ደደብ!" ብሎ ደነፋ። ዳስተሩን አንስቶ አንዴ እጁን ሲያስወነጭፈው ሀይለስላሴን ለሁለት እማሆይ ቴሬሳን አናታቸውን ገመሳቸው። አጠፋፍቶ ማስተማሩን ቀጠለ። ምስጋናው ከዛ በኋላ እንኳን ሰሌዳ ላይ ወረቀት ላይ ሲስል አላስታውስም።

ብዙ ዓመታት አለፉ። አንድ ቀን አዲስ አበባ ፒያሳ መርከብ የምትባል ምግብ ቤት ምሳ በልተን ስንወጣ በር ላይ አንድ የጎዳና ተዳዳሪ በፌስታል ፍርፋሪ ሲበላ አየሁ ምስጋናው ነበር። ቢጎሳቆልም አልጠፋኝም። ዛሬ በምን አስታወስኩት? አንድ አሜሪካዊ ህፃን ሰሌዳ ላይ በቾክ የሳለው ስእል በአስተማሪዎቹና በትምህርት ቤቷ ርዕሰ መምህር ስለተደነቀ በቀስታ ሰሌዳውን አንስተው አንድ ቢሮ ግድግዳ ላይ እንደሰቀሉት አነበብኩ። ስዕሉ ለዓመታት እንዲቆይ የሆነ ነገር እናስደርጋለን ብላለች ርዕሰ መምህርቷ። አገር ባከበረቻቸው ትከብራለች ባከሸፈቻቸው ትከሽፋለች። ይህ ሒሳብ የገባቸው ብፁአን ናቸው። ለትውልድ ፍቅር ያወርሳሉና።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

30 Oct, 04:19


ጠላ እየጠጣን ከጓደኞቼ ጋ ተሰባስበን እየቀደድን ሳለ ፦

ምድር ላይ የትኛውን ገጠመኝህን በይበልጥ ትወዳዋለህ የሚል ቀደዳ ጀመርን

ፍሬንድ ቀጠለ

"አንድ እለት እሁድ ጠዋት እናቴ ቡና እየጠጣች ፣ እየመከረችኝ ፣ እየመረቀችኝ ፣ እየሰደበችኝ ሳለ

በጣምምም ደስስ የሚልሽ ምን ብታገኝ ነው አልኳት አጠያየቄ ድንገት ነበር

ላሊበላ ፣ አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ብሄድ ደስ ይለኛል አለቺኝ

ፊቷ ላይ ያለው ምኞት የደስታ ዳር ይመስል ነበር። ። በነጋታው ስጣደፍ ሄጄ ቢሮ አንድ መቶ ሺ ብር ተበደርኩ ፍቃድ ወሰድኩ

ሎተሪ ደረሰኝ ብያት ላሊበላ ፣ አክሱም ጽዮን ፣ ውቅሮ ማርያም ካዲ ወሰድኳት ደስስ አላት ፀለየች ፣ ለነዲያን መፀወተች ፣ እጄን ይዛ መረቀቺኝ ።

ከዛ ከተመለስን በኋላ ሶስት ወርም አልቆየች ትንሽ አሞት ሞተችብኝ። ሳለቅስ ፣ ሳዝን ያፅናናኝ እና ያበረታኝ ህልሟን ማሳከቴ ነበር

ቀጠለ ሌላ ፍሬንድ ፦

"አንድ ቀን ክላስ ቀጥቼ ዩኒፎርሜን እንደለበስኩ ጠላ ቤት ደቅ ብዬ አባቴ ከጓደኞቹ ጋር ከች አለ ሳየው ስካሬ ጠፋ ።

ልጄ ነው ብሎ ለፍሬንዶቹ አስዋወቀኝ ። ሃይለኛ ስለነበር እዛው ካልገደልኩ ይላል ብዬ ነበር። ምንም አላለኝም ። እንደውም የጠጣሁበትን ከነ ፍሬንዶቼ ከፈለልኝ ። ቀድሜው ወጣሁ ፦

አላመንኩትም የሚገድለኝን አገዳደል እያሰብኩ ስፈራ ስቸር እቤት አምሽቼ ገባሁ ። እሱ ምንም አላለኝም ።

በሳምንቱ "ጋሻው ዛሬ ትምህርት የለህም አይደል "

"አዎ"
"በቃ ዛሬ አብረን እንዋል አለኝ" እሺ ብዬው የሚሰራበት
አብረን ሄድን

ውሎውን አዋለኝ ። የሆነ ህንፃ ይጠብቃል ፣ ህንፃው ጋ የሚቆም መኪና ይጠብቃል ፣ መኪና ያጥባል ።

የጠበቀበትን እና ያጠበበትን ብር እንዲሰጡት ደጅ ይጠናል ፤ ትንሹም ትልቁም ይጠራዋል ፣ ያዙታል ያን ቀን አባቴ በጣም አሳዘነኝ

ከፊቱ ገሸሽ ብዬ አለቀስኩ

እንዴት እንደሚያሳድገኝ ያኔ ነው የገባኝ ። ምን እያለ እንደመከረኝ ፣ በእኔ ጉዳይ ለምን እንደሚናደድ ገባኝ

የዛ ቀን ህይወቴ ተቀየረ ።

ሌላ ፍሬንድ ቀጠለ ፦

"አንድ ቀን እቃ ጠፍቶኝ ቤታችንን ሳምሰው
የታናሽ እህቴ ዲያሪ አገኘሁት በማላውቀው ምክንያት የማስሰውን ነገር ትቼ ደቅ ብዬ ማንበብ ስጀምር ።

ጥጋቤ ፣ ድፍረቴ እልሄ ተነፈሰ ። የግሩፕ ጠብ አጓጉል ውሎዬ ጣጣ ለመጀመሪያ ጊዜ ገባኝ። ለመጀመሪያ ጊዜ መፍራት ጀመርኩ ፤ ለቤተሰባችን ምን ያህል እንደማስፈልግ ማስታወሻዋ ነገረኝ"

ለካ አንዳንድ ቀን ብቻውን ዘመን ያህላል !!
© Adhanom Mitiku

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

29 Oct, 17:30


ዛሬ ከሰማኋቸው አባባሎች ጥቂቱን እንካችሁ ልበላችሁ
1, Thinking is the most difficult task.
2, If you forget, you didn't learn.
3, ወደ ዩንቨርስቲ የገባችሁ ጊዜ ነፃነታችሁን ታጣላችሁ ። 😅💯
4, የሰው ልጅ ጠላቱ እራሱ ነው።
5, የሰው ልጅ ጭንቅላት በባህሪው ሰነፍ ነው።
6, ማየት ማመን አይደለም።
Credit - Mr, Berhanu Getachew

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

28 Oct, 05:47


Check our Sunday edition out this morning in #AddisAbeba, #Ethiopia and available online at https://addisfortune.news

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

27 Oct, 10:23


"ልማድሽ ነው"

"ባለፈው እንደእብድ ያረገሽን ዘፈን አገኘሁት እኮ ቆይማ ልላክልሽ" ብሎ ስልኩን ሊያወጣ ሲል "የትኛውን ዘፈን አለችው ግራ ተጋብታ

"እንደውም ዜማውን ብቻ የሆነ ካፌ ሰምተሽው ምነው ባገኘሁት ብለሽ ሲቆጭሽ የነበረው ዘፈን..." አላት ቅሬታ እየተነበበት "እ እሱ ነው እንዴ? ፈልጌ ሳጣው ሌላ አገኘሁ እኮ እንዴት ደስ እንደሚል ግጥሙ ብትል ዜማው..." እያለች ስታብራራለት በትዝብት ሲያያት ቆየና

"እ ደስ አይልም?!" አለችው ዘፈኑን ከፍታ ምላሹን እየጠበቀች "ልማድሽ ነው አንዱን ስታጪ ሌላ መውደድ" አላት

ስለዘፈኑ መስሏት ምንም አላለችም ነበረ ኋላ ማታ ላይ ሲቆረቁራት አደረች እንጂ...

ናኒ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

17 Oct, 12:20


(የገጣሚ ክፋቱ)

ገጣሚ ክፉ ነው
ተለየሁኝ ብሎ መች በቋት ይለፋል
ፍቅርን አንቅሮ በብዕር ይተፋል
ብያት ነበር ያኔ
ይሄው ስትለየኝ፣ ቀለም በጠበጥኩኝ
ተለየችኝ የሚል፣ አስር ግጥም ፃፍኩኝ
(ተፋኋት መሰለኝ)
ከልቤ ከረጢት እንባዬ አለቀ
የነከርኩት ቀለም ከእጄ ደረቀ።


(እንግዳዬሁ ዘሪቱ) 🔥🔥❤️🔥🔥

ገጣሚ አይደለሁም👆👆

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

14 Oct, 16:45


#አስገራሚ_እውነታዎች

ስለ መጽሐፍ አንባቢዎች አምስት አስገራሚ እውነታዎች እነሆ፡-

1. የተሻሻለ ርህራሄ፡- አዘውትረው አንባቢዎች፣ በተለይም ልብ ወለዶች፣ ብዙውን ጊዜ የበለጠ ርህራሄ እና የሌሎችን ስሜት በደንብ ይገነዘባሉ።  ጥናቶች እንደሚያሳዩት ስለ ውስብስብ ገጸ-ባህሪያት ማንበብ ማህበራዊ ክህሎቶችን እና ስሜታዊ እውቀትን ለማዳበር ይረዳል.


2. የተሻሻለ የአንጎል ግንኙነት፡- ማንበብ አንጎልን ያነቃቃል እና የነርቭ ግኑኝነትን ያሻሽላል በተለይም ለቋንቋ እና ምናብ ተጠያቂ በሆኑ አካባቢዎች።  ይህ የማስታወስ ችሎታን እና የእውቀት (ኮግኒቲቭ) ተግባርን ያሻሽላል, በእርጅና ጊዜ የእውቀት ማሽቆልቆልን እንኳን ይከላከላል.


3. የጭንቀት ቅነሳ፡- ስድስት ደቂቃ ብቻ ማንበብ ጭንቀትን እስከ 68% ሊቀንስ እንደሚችል የሱሴክስ ዩኒቨርሲቲ ጥናት አመልክቷል።  እንደ ሙዚቃ ማዳመጥ ወይም በእግር መሄድ ካሉ ሌሎች የመዝናኛ ዘዴዎች የበለጠ ውጤታማ ነው።


4. የዕድሜ ልክ ትምህርት፡ አንባቢዎች ተፈጥሯዊ የማወቅ ጉጉት እና የዕድሜ ልክ ትምህርት ቁርጠኝነት ይኖራቸዋል።  ከመደበኛ ትምህርት በላይ እውቀትን ይቀበላሉ።


5. ረጅም ዕድሜ መጨመር፡- የዬል ዩኒቨርሲቲ ጥናት እንደሚያመለክተው በቀን ለ30 ደቂቃ መጽሐፍትን የሚያነቡ ሰዎች ከማያነቡ ሰዎች በአማካይ በሁለት ዓመት ይረዝማሉ።  ንባብ የአእምሮ ማነቃቂያን ያበረታታል እና አእምሮን በንቃት ይጠብቃል ፣ ይህም ረጅም ዕድሜ እንዲቆይ አስተዋጽኦ ያደርጋል ።
Jafar books

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

12 Oct, 13:04


#Amazingfacts

1. ብዙ የተተረጎመ መጽሐፍ፡- “The little prince” በአንቶኒ ዴ ሴንት-ኤክሱፔሪ ከ300 በላይ ቋንቋዎች እና ቀበሌኛዎች ተተርጉሟል፣ ይህም በዓለም ላይ በጣም ከተተረጎሙ መጻሕፍት አንዱ ያደርገዋል።

2. ረጅሙ ልቦለድ፡ "In Search of Lost Time" በማርሴል ፕሮስትት የተፃፈው ረጅሙ ልቦለድ ነው: : ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ቃላት ይዟል።


3. እጅግ ውድ የሆነው መጽሀፍ :-የሊዮናርዶ ዳ ቪንቺ "Codex Leicester" በቢል ጌትስ በ 1994 በ 30.8 ሚሊዮን ዶላር የተገዛ ሲሆን ይህም እስከ አሁን ከተሸጠው ውዱ መፅሃፍ ነው።


4. የዓለማችን ትልቁ ቤተ መፃህፍት፡ በዋሽንግተን ዲሲ የሚገኘው የኮንግረስ ቤተ መፃህፍት በዓለማችን ትልቁ ቤተ-መጻሕፍት ነው፡ በስብስቡ ውስጥ ከ170 ሚሊዮን በላይ ዕቃዎች፣ መጻሕፍትን፣ የእጅ ጽሑፎችን እና ቅጂዎችን ጨምሮ።


5. ቃላቶች የሌሉ መፅሃፍት፡- ስዕሎችን እና ምሳሌዎችን ብቻ በመጠቀም ሙሉ ታሪኮችን ያለ አንድ ቃል የሚናገሩ እንደ ሻውን ታን "The Arrival" ያሉ መጽሃፎች አሉ።

💥 ከጃዕፈር መፅሀፍት

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

10 Oct, 20:23


በደስታ በምትፈነድቅበት ወቅት ለጥቂት ጊዜ ወደ ልብህ ውስጥ ጠልቀህ ተመልከት ያስደሰተህ ነገር ሲያሳዝንህ የከረመ መሆኑን ትረዳለህ••••ደስታና ሀዘን በአንድነት ይኖራሉ።አንዱ አብሮህ ሲውል ሌላው አልጋህ ላይ ተኝቶ እንደጠብቅህ አትዘንጋ።
ካህሊል ጀብራን

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

10 Oct, 04:37


*ከተለያየን ከወር በኋላ...

ስልኬን አንስቼ...
የመጨረሻ መልእክትሽን አነበብኹት ።
ጎበዝ ፀሐፊ እንደሆንኹ ታውቂያሽ...ነገር ግን እስካሁን መልሱን አልፃፍኹልሽም ።


"እንለያይ ! ይብቃን ፤ ከዚህ ወዴት እንደምንሄድ አላውቅም።" ነበር መልእክትሽ ።

እስካሁን አልመለስኹልሽም...
መልእክትሽን ካልመለስኹ አንለያይም ብዬ ነበር ያሰብኹት ።

ግን...


ከ ተ ቀ ደ ደ ው ማስታወሻ
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

09 Oct, 20:13


ሕይወት ቀጣይነት ያለው ፈተና፣ ተስፋ አስቆራጭ መሰናክሎችን የያዘ እንደሆነ ተረዳ፡፡ ይሁን እንጂ እውነተኛ መሪ ለተስፋ መቁረጥ ወይም ለማማረር ፈጽሞ እጁን አይሰጥም፡፡ ከማጉረምረም፣ ሰበብ ከመደርደር ወይም ቀላል በሆነ ብሎ ከመመኘት ይቆጠባል፡፡ ይልቁንም የሄንሪ ፎርድ ቃላቶችን ያስታውሳል፣ “መውደቅ፣ በጥበብ እንደገና ለመጀመር እድል ይሰጠናል”

✍️ብሪያን ትሬሲ

📚@Bemnet_Library

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

08 Oct, 18:58


"ነገ ጥሩ ይሆናል..." የሚለው ተስፋ ከልቤ ሲሟጠጥ ፤ "ይሄም ያልፋል " በሚለው ቃል ደግሞ ልቤ ይፅናናል።



ነገ የራሱ ጉዳይ !
©ሶፊ

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

08 Oct, 09:06


የአባት ምክር

በአንድ ወቅት አንዲት ሴት ልጅ ህይወቷ የተመሰቃቀለ እንደሆነ እና አንዱን ችግር ስትፈታ ሌላ ችግር እንደሚገጥማት፤ መኖር እንደከበዳታ እና ከዚህ በላይ ችግሮቿን መቋቋም እንደማትችል አቤቱታዋን ለአባቷ አቀረበች፡፡አባቷ የምግብ ሰራተኛ ነው፤እናም ወደ ማብሰያ ክፍል ይዟት ሄደ፡፡ ሶስት ድስቶችን ውሃ ሞልቶ እሳት ላይ ጣዳቸው፡፡በድስቶቹ ውስጥ ያለው ውሃ መፍላት ሲጀምር በአንዱ ድስት ውስጥ ድንች፤በሌላኛው ውስጥ እንቁላል፤በሶስተኛው ውስጥ ደሞ ቡና ጨመረባቸው እና ከደነው።እናም ምንም ሳይናገር መጠበቅ ጀመረ፡፡ልጁ መነጫነጭና ትዕግስት በጎደለው መልኩ ምን ሊያረግ እንደሆነ ለማየት መጠበቅ ጀመረች፡፡
ከ20 ደቂቃ በኋላ እሳቱን አጥፍቶ ድንቹን፣እንቁላሉን አውጥቶ በአንድ ሰሃን አስቀመጠ፡፡ ቡናውን በሲኒ ቀድቶ አስቀመጠ፡፡

አባት ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀ "ልጄ አሁን ምን ይታይሻል? በማለት ጠየቃት።ልጅ "በቁጣ ስሜት ሁና ድንች፣እንቁላል፣ ቡና'' አለች፡፡"በደንብ ተመልከች፤ድንቹን ንኪው" አላት።እንዳላት አድርጋ ድንቹ ጥንካሬውን እንዳጣ ተገነዘበች፡፡ ''እንቁላሉንም ስበሪው" አላት፡፡ሰበረችው ነገር ግን አስኳሉ ሌላ ጠንካራ እና የሚያቃጥል አካል ሰርቷል።በስተመጨረሻ ከቡናው ፉት እንድትል አዘዛት።እሷም ቀምሳ ደስ የሚለው ጣዕሙ የፊቷን ፈገግታ
ሲቀይረው ታወቃት፡፡ ''አባቴ ይህ ምንድን ነው ?' አለች፡፡
አባት ማብራራት ጀመረ፡፡ "ድንቹ፣ እንቁላሉ እንዱሁም የቡናው ዱቄት ሁሉም እኩል የፈላ ውሃ ውስጥ ነው የገቡት፡፡ ነገር ግን ሁሉም ለፈላው ውሃ የሰጡት ምላሽ የተለያየ ነበር፡፡ድንቹ በፊት ጠንካራ ነበር፤ነገር ግን በፈላ ውሃ ሲፈተን ጥንካሬውን አጥቶ ልፍስፍስ ሆነ፡፡እንቁላሉ በፊት በቀላሉ ከተሰበረ ሜዳ ላይ የሚፈስ ልፍስፍስ አስኳል ነበር፡፡ነገር ግን በፈላ ውሃ ሲፈተን ውስጡን አጠንክሮ መጣ፡፡ከሁሉም የሚገርመው ግን የቡና ዱቄቱ ነው፡፡በፈላ ውሃ ሲፈተን እራሱ ውሃውን ወደ ጣፋጭን መልካም ጠረን ቀይሮ አዲስ ነገር ፈጠረ፡፡
አንቺ የትኛው ነሽ ? በማለት ልጁን በብልሃት አስረድቶ አስተምሯታል።

ችግር ሲገጥማችሁ የእናንተ ምላሽ ምንድን ነው? እንደ ድንቹ መልፈስፈስ? ወይስ እንደ እንቁላሉ ውስጥን ማጠንከር? አልያም ችግሩን ለአዲስ ነገር መፍጠሪያ መጠቀም ? በህይወት ውስጥ ነገሮች በአካባቢያችን ይከናወናሉ፤ ነገሮች በእኛ ላይ ይደርሳሉ፤ ነገር ግን ትልቁና ወሳኙ በእኛ ውስጥ የሚከናወነው ነገር ነው!" የትኛው ነህ ?/ነሽ ??

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

05 Oct, 09:10


ፍቅር ለእዉነት ቦታ የላትም። መወደድ ምናብ ይጠይቃል። የሚደንሱ ልቦች ፣ የሚጠለቁ ጭንብሎች ይፈልጋል። 

ፍቅር ከራስ ጋር የሚደረግ ሽንገላ ነዉ። በአፈቀርከዉ አይን ዉስጥ የምታየዉ የምትሻዉን ፥ የምትወደዉ የጎደለህን ነዉ። መዉደድ ከእዉን ለህልም ይዛመዳል።

"Love is a mutual misunderstanding" እንዲል Oscar Wilde!



@samuel_dereje

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

03 Oct, 15:34


📌ዝክረ- ኤልያስ መልካ አምስተኛ ዓመት !

ተወዳጁ የሙዚቃ አቀናባሪ ኤልያስ መልካ ካረፈ ነገ አርብ መስከረም 24 2017 ዓ.ም አምስት ዓመት ይሞላዋል።

በኤልያስ መልካ አድናቂዎች ህብረት የተዘጋጁ እና የኤልያስ መልካን አምስተኛ ዓመት የሚዘክሩ መርሐግብሮች በቀጣይ ቀናት ይካሄዳሉ።

ከነዚህም የመታሰቢያ መርሐግብሮች ውስጥ ነገ ከጠዋቱ 3:30 ጀምሮ በጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን በኤልያስ መልካ አድናቂዎች የአበባ ጉንጉን የማኖር ሥነሥርዓት ይከናወናል ።

መምጣት የሚፈልግ ሁሉ በቦታው መገኘት ይችላል ቦታው ዊንጌት አካባቢ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን ነው ።

ለተጨማሪው: https://t.me/EventAddis1

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

27 Sep, 08:54


#ደስ_የሚል_ወሬ 💖

. #ክንፋም_ከዋክብት - የ50 ገጣሚያን ሥራ
. #ነገ #ሐሙስ ከሕትመት ይወጣል __

መጽሐፍ የመቀበል [የቡና ሠዐት] ይኖረናል።

መጽሐፉ በቅድመ ሽያጭ ላይ ነው።
* ሰይፉ ወርቁ 1000420583528 [0924913036]
* ጌታቸው ዓለሙ 1000143312244 [0911125788]

👉 #ደረሰኙን በቴሌግራም ወይም በሜሴንጀር ይላኩልን።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

21 Sep, 21:08


የመጨረሻ ክፍል

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

21 Sep, 10:00


በኢቲቪ እየተላለፈ ያለው የፍቅር እስከመቃብር ፊልም በፍርድ ቤት እግድ ወጣበት ‼️

የደራሲ ክቡር ዶ/ር ሐዲስ ዓለማየሁ ወራሽ ፍርድ ቤት የነበራቸውን ክርክር መነሻ በማድረግ የደራሲው ስራ የሆነውን ፍቅር እስከ መቃብር የተሰኘ ድርስት 1ኛ ተጠሪ ወደ ፊልም ቀይሮ ለህዝብ ከማሰራጨት ድረጊቱ እንዲታገድ አቤቱታ አቅርበዋል፡፡ በቀረበው አቤቱታ ላይ ይግባኝ ባዮች አስተያየት እንዲያቀርቡ በተሰጠው ትእዛዝ መነሻነት 1ኛ ይግባኝ ባይ መስከረም 6 ቀን 2017 ዓ.ም ጽፎ ባቀረበው አስተያየት እግድ የሚሰጥ ከሆነ ኪሳራ እንደሚደርስባቸው በመዘርዘር እግዱ ሊሰጥ አይገባም በማለት ተከራክረዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የቀረበውን ክርክር እና ማስረጃ ፍርድ ቤቱ መርምሮ ተክታዩን ትእዛዝ ሰጥቷል፡

👉ትእዛዝ

1/ በዚህ መዝገብ ላይ የቀረበው ክርክር ተመርምሮ ውሳኔ እስኪሰጥ ድረስ ለክርክሩ መነሻ የሆነውና ወደፊልም የተቀየረው ፍቅር እስከ መቃብር የድርሰት ስራ ለህዝብ እይታ የሚሰራጭ ከሆነ የቅጅ መብት አለኝ በሚሉት መልስ ሰጭዋ ላይ ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ሊደርስባቸጡ የሚችል ከመሆኑም በላይ የማይተካ የሞራል ጉዳት ሊደረስባቸው ስለሚችል በዚህ መዝገብ ላይ የቀረበው ክርክር ተመርምሮ ውሳኔ ለመስጠት እስከተያዘው ቀጠሮ ማለትም እስከ #ህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ወይም ከወዲሁ ትእዛዙ መነሳቱ እስከሚገልጽ ድረስ ወደ ፊልም የተቀየረው ተጠቃሹ የድርሰት ስራ በማናቸውም መንገድ ለህዝብ እይታ እንዳይቀርብ እንዳይሰራጭ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ/ ቁጥር 154 መሰረት ታግዷል፡፡

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

17 Sep, 18:46


ክፍል 3 ........ ይቀጥላል
share and like

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

12 Sep, 20:05


የሞት መድሀኒት 2 ለመለቀቅ በደንብ like ማግኘት ይጠበቅበታል።

ሼር እና ላይክ አድርጉ።

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

12 Sep, 12:37


አንዲት ሴት የተራበ ትንሽ እባብ መንገድ ላይ አገኘች።

እናም ከሚሰቃየው እራብ  ልታድነው ወሰነች። 

ወደ ቤቷ ወሰደችውና አስጠለለችው።እባቡም አድጎ እስኪለምዳት  ድረስ መመገብ ጀመረች።

ወደ ቤት በገባችበት ቦታ ሁሉ ከኃላ ይከተላታል። 
ማታ ላይ  በሙቀቷ እየተደሰተ አልጋው ላይ ከጎኗ ይተኛል ።

ዓመታት አለፉ እና እባቡ አደገ።
🌼🌼🌼🌼
እናም አንድ ቀን ያቺ ሴት እባቡ ባልታወቀ ምክንያት መብላት በማቆሙ ተገረመች።

አዛኟ ሴት እባቡን እንዲበላ ለማድረግ ብዙ ሞክራለች።
እሱ እንዳይሞትና እንዳይጠፋ  በመፍራት ፤ እባቡ ግን እምቢ አለ።

እና ሙከራዎቿ ሁሉ አልተሳኩም። 

- እባቡ ለመመገብ ፈቃደኛ ባለመሆኑ ለብዙ ሳምንታት በዚህ ሁኔታ ውስጥ ቆየ።ነገር ግን በቀን ይከተላታል ።ማታ አልጋዋ ላይ ከጎኗ ይተኛ ነበር።   ሰውነቷ ላይ በመጠምጠም ሙቀት ከሰውነቷ እየወሰደ አብሯት ይተኛል ።

- በመጨረሻም ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ሴትየዋ ወደ የእንስሳት ሐኪም ወስዳ እንዲመረምረው ወሰነች።  ምናልባት ታሞ ህክምና ያስፈልገዋል ፤ በሚል እሳቤ። 

ሐኪሙ እባቡን ከመረመረ በኋላ ወደ ሴቲቱ ዞር ብሎ ጠየቃት።
🌼🌼🌼🌼
ሃኪሙ :- እባቡ ላይ የምግብ ፍላጎት ከማጣት እና ከምግብ ከመታቀብ በስተቀር ሌሎች ምልክቶችን አስተውለሻል ?

ሴትየዋ መለሰች፡- እረ የለም። 

- ዶክተሩ በድጋሚ ጠየቃት: -  አሁንም ለሊት ካጠገብሽ ይተኛል  ?
- ሴትየዋ መለሰች:-  አዎ ፡ እሱ ከእኔ ጋር በጣም ይጣበቃል። ወደ ቤት ውስጥ በሄድኩበት ሁሉ ይከተለኛል።  ሁልጊዜ ማታ በአጠገቤ አልጋ ላይ ይተኛል።

- ዶክተሩ ጠየቃት፡- አንዳንድ ጊዜ ከጎንሽ ሲተኛ በሰውነትሽ ላይ እንደሚጠመጠም አላስተዋልሽም?

- ሴትየዋ በጣም ተገርማ ለሐኪሙ: -  አዎ ፡ አዎ  ፡ ይጠመጠምብኛል አለችው።

በቅርብ ጊዜ በህመሙ ምክንያት  ሙቀት በመፈለግ  እንዳዝንለት  አንዳንዴ በእንቅልፍዬ ላይ እያለሁ ይጠመጠማል። ሲነቃም በአይኑ ይከተለኝና ምግብ ለሱ ለመስጠት  እቸኩላለሁ። እንደ አለመታደል ሆኖ ለመብላት ፈቃደኛ አልሆነም እና በቦታው ይቀመጣል።

- ዶክተሩ ፈገግ አለና እንዲህ አላት፡ -

እመቤት ፦  ይህ እባብ አልታመመም ሊበላሽ ነው እንጂ!!!

እሱ
እባቡ አንችን ለመብላት አእስኪችል ድረስ ለመራብ እየሞከረ ነው።

እንዲሁም ከአንቺ ጋር በፍቅር ሳይሆን በሰውነትሽ ላይ የሚጠቀለለው  አንቺ እንደምታስቢው ሙቀት እና ርህራሄ ፍለጋ ሳይሆን  ከሆዱ መጠን ጋር የሰውነትሽ መጠን ለመለካት እየሞከረ ነው።

ይህም ሆዱ የአንቺን መጠን የሚበላ ምግብ ለማስተናገድ  በትክክለኛው ጊዜ ሊያጠቃሽ እየተዘጋጀ ነው።

እመቤቴ  ይህን እባብ በፍጥነት አስወግጅው።  ብሎ መከራት !!

                     ከታሪኩ የምንማረው ፡-
- አንዳንዶች በዙሪያው ያሉትን በፍቅር፣ በደግነት ወይም በበጎ አድራጎት ሊለውጥ ይችላል ብለው ያስቡ ይሆናል።

ነገር ግን በአንዳንዶች ውስጥ በተፈጥሮ መርዝ ተሸክመው ጊዜ የሚጠብቁ ብዙ ሰዎች አሉ እናም ይጠንቀቁ ።

ፈጣሪ ከክፋታቸው ይጠብቀን ።
Bini Berhe
🌼🌼🌼🌼
"ማንበብ ፋሽን ነው።"
Join us @noahbookdelivery

ሐሽማል ቤተ-መዘክር

11 Sep, 18:04


በዓልና ማንነት የሆነ አይነት አንድ መመሳሰል አላቸዉ። እኛን እኛ የሚያደርገን ትዉስታቸን ብቻ አይደለም። ትናንቱን የረሳ አንድ ህመምተኛ ሌላ ሰዉ ሆኗል አንልም። የሆነ መንፈሱን ግን ያጣል። ጎደሎነት አለዉ። ሰዉየዉ ራሱን ሆኖም።

ካምፓስ እያለሁ አንድ ሁለት በዓል አሳልፊያለሁ። ያለ ቤተሰብ በዓል ያ ስሜት አለዉ። አዘቦትነት።

አዲስ አመት በምስርም ለዛ ይጠጋጋል። በዓል ነዉ ግን መንፈሱ የለዉም። የሆነ የጾም ቀን እሁድ . . .


እና መስከረም አንድ ነገ ነዉ :)

📍 ዥንጉርጉር