Amhara Police Commission @amharapolicecommission Channel on Telegram

Amhara Police Commission

@amharapolicecommission


Peace keeper

Amhara Police Commission (English)

The Amhara Police Commission is a Telegram channel dedicated to promoting peace and security in the region. With the username @amharapolicecommission, this channel serves as a platform for the Amhara Police Commission to engage with the community, provide updates on law enforcement efforts, and share important safety information. Who is it? The Amhara Police Commission is an official law enforcement agency responsible for maintaining peace and order in the Amhara region of Ethiopia. They work tirelessly to ensure the safety and security of all residents, and this Telegram channel allows them to directly communicate with the public. What is it? This channel is a valuable resource for residents of the Amhara region who are looking to stay informed about law enforcement activities, public safety initiatives, and community outreach programs. By following @amharapolicecommission, users can receive real-time updates on crime prevention tips, emergency alerts, and information on how to report suspicious activities. Whether you are a resident of the Amhara region or simply interested in staying informed about law enforcement efforts in Ethiopia, the Amhara Police Commission Telegram channel is a must-follow. Join today to support their mission of being peacekeepers in the community and help build a safer environment for all.

Amhara Police Commission

14 Feb, 16:25


"ሳናውቅ በስህተት የበደልነውን ህዝብ ለመካስ ዝግጁ ነን።" በሰላማዊ መንገድ እጃቸውን ለመንግስት የሰጡ ታጣቂ ሃይሎች

በምዕራብ ጎንደር ዞን አዳኝ በአገር ጫቆ ወረዳ በጫካ የነበሩ ታጣቂዎች መንግስት ያቀረበውን የሰላም ጥሪ ተቀብለው ለመንግስት እጃቸውን በሰላም ሰጥተዋል።

ታጣቂዎቹ እንዳሉ፤ በተሳሳተ መንገድ ተገደን የገባንበት መንገድ ስህተት መሆኑን ተረድተን መንግስት ያቀረበውን የሰላም አማራጭ ተቀብለን መጥተናል። በቀጣይም ሳናውቅ በስህተት የበደልነውን ህዝብ ለመካስ ዝግጁ ነን ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

መረጃው የአዳኝ አገር ጫቆ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ነው።
ተጨማሪ መረጃዎችን ከአማራ ኮሙኒኬሽን የተለያዩ የመረጃ መረቦች ቀጣዮቹን ሊንኮች በመጫን ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

Amhara Police Commission

14 Feb, 10:58


የ 7 ዓመት ህፃን የደፈረው ግለሰብ ከማንኛውም ህዝባዊ መብቶች እንዲታደግ ተወሰነበት

አማራ ፖሊስ፡የካቲት 07 ቀን 2017 ዓ.ም

በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ የሰባት ዓመት ህፃን ልጅ አስገድዶ የደፈረው በእስራት መቀጣቱን የቃሉ ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ።
ተከሳሹ በእስራት ሊቀጣ የቻለው ታህሳስ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ቃሉ ወረዳ 029 ቀበሌ ልዩ ቦታው ገረገራ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ተከሳሽ ከድር ይመር መሀመድ የ 7 ዓመት ህፃን ልጅ አስገድዶ በመድፈሩ የወረዳው ፖሊስ ከማህበረሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ካደረገ በኋላ የምርመራ መዝገቡን በሰውና በቴክኒክና በታክቲክ ማስጃ ካጠናቀረ በኋላ መዝገቡን ለሚመከተው የፍትህ አካል ልኳል።

የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍረድ ቤትም ጉዳዩን ሲመረምር ከቆዬ በኋላ ተከሳሹ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ የካቲት 04 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በ17 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ እና ለ 4 ዓመት ያህል ከማንኛውም ህዝባዊ መብቶች እንዲታገድ ተወስኖበታል ሲል የቃሉ ወረዳ ፖሊስ ኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ክፍልን ጠቅሶ የደቡብ ወሎ ዞን ፖሊስ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ነው።

Amhara Police Commission

13 Feb, 12:53


በፍትህ ስርዓቱ የሚታዩ ጉድለቶችን ለማሻሻል ሳይንሳዊ የምርመራ ዘዴን ማጠናከር እንደሚገባ ተገለፀ፡፡

የአማራ ክልል ፖሊስ የፎረንሲክ ላብራቶሪ በ2017 ግማሽ ዓመት 4515 ናሙናዎችን በመመርመር ለፍትህ ስርዓቱ የሚጠበቅበትን አወንታዊ ሚና ተወጥቷል፡፡
አማራ ፖሊስ:የካቲት 6/2017 ዓ.ም

ፎረንሲክ ምርመራ በወንጀልም ይሁን በፍትሐብሄር ክርክር ጉዳይ የምስክርነት ማስረጃዎችን በሳይንሳዊነት ማግኘት፣ መተንተን፣ ማቅረብ እና እውነትን ለመፈለግ የሚደረግ ሲሆን ለፍትህ ስርዓቱ ታማኒነት እጅግ ወሳኝና አስፈላጊ ከሚባሉ ጉዳዮች ዋነኛው ነው፡፡
ፎረንሲክ ምርመራ የሞት ምክንያትን ማረጋገጥ ፣የደም፣ የጸጉር፣ መድኃኒቶች፣ መርዝ፣ የኮምፒዩተር፣ ስልክ፣ ኢንተርኔት እንዲሁም የተሳሳቱ ሰነዶችን መመርመርን የሚጠቃልል ሲሆን እውነት ላይ ለመድረስ የተሻለው አማራጭ መሆኑን የዘርፉ ባላሙዎች ይመሰክራሉ፡፡ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አራት የፎረንሲክ ምርመራ ክፍሎችን በማቋቋም አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን በወንጀል ምርመራ ዘርፍ የፎረንሲክ ምርመራ ም/ዘርፍ ኀላፊ ኮማንደር መካሻ ተክለ ብርሃን ሀሰተኛ ማስረጃን ለማስቀረት ሳይንሳዊ ምርመራ ላይ ማተኮር ይጠበቅብናል ብለዋል፡፡
በግማሽ ዓመቱ ለምክትል ዘርፍ ከቀረቡት 5009 ተመርማሪ ሰነዶችና ናሙናዎች 4515 የሚሆኑትን ምርመራቸውን በማጠናቀቅ ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላኩን ያነሱት ኮማንደር መካሻ የፎረንሲክ ምርምራ ተደራሽነትን ለማስፋ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አንስተዋል፡፡
የፎረንሲክ ምርምራ በአጠቃላይ የፍትህ ስርዓቱ የሚኖረውን ሚና በውል ተረድቶ በጋራ መስራት ይገባል የሚሉት ኮማንደር መካሻ ተክል ብርሃን አገልግሎት ፈላጊዎች ተቋሙ እየሰጣቸው በሚገኙ የፎረንሲክ ምርመራዎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡

Amhara Police Commission

11 Feb, 08:28


የሕዝቡን ሰላም እና ደኅንነት ለመጠበቅ  ጠንካራ ሥራ መሠራቱን የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ገለጸ።

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ፤ የዞኑ ሰላምና ጸጥታ መምሪያ የ6 ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫ የውይይት መድረክ በሁመራ ከተማ አካሂዷል።

በግምገማው የተገኙት የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ምክትል ኅላፊ ኢንስፔክተር ጌታቸው ሙሉጌታ  የወልቃይት ጠገዴን የወሰን እና የማንነት ጥያቄን አሳልፎ የሚሰጥ መሪ የለም ብለዋል።

ሕዝቡ ወዳጅ እና ጠላቱን ለይቶ ለመብቱ እና ለማንነቱ እንዲቆም ማንቃት ፣ ማደራጀት እና ማንቀሳቀስ እንደተቻለም ተናግረዋል። ከውጭም ሆነ ከውስጥ ያለ ኅይል በጦርነት የሚያመጣው መፍትሄ የለም ያሉት ኢንስፔክተሩ ፍላጎቱን በኅይል ማሳካት የሚፈልግ አካል ላይም የተጠናከረ እርምጃ ይወሰድበታል ብለዋል።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ሕዝብን ነቅቶ የሚጠብቅው የጸጥታ ኀይል፤ ለመብት እና ለማንነቱ የሚታገል መሪ እና ተደራጅቶ የሚያደራጅ ጠንካራ መዋቅር ያለው መኾኑንም ተናግረዋል።

የወሰን፣ የማንነት እና የድንበር ጥያቄዎቹ   ለድርድር የሚቀርቡ  አለመኾናቸውን አንስተዋል። ዞኑ በስድስት ወራት የጸጥታ ሥራ አፈጻጸሙ የሕዝቡን ሰላም እና ደኅንነት በመጠበቅ፣ ሕግ እና ሥርዓትን በማጽናት ረገድ ጠንካራ አፈጻጸም ማስመዝገቡን  ገልጸዋል።

በክልልሉ የተፈጠረው የጸጥታ ችግር በዞኑ አንዳንድ አካባቢዎችም የተከሰተበት ወቅት እንደነበር ያነሱት ምክትል ኀላፊው በጸጥታ መዋቅሩ እና በዞኑ አጠቃላይ የመሪዎች ቁርጠኝነት ችግሩን ማስተካከል መቻሉንም ተናግረዋል።

ዝርፊያን እና እገታን በማስቆም ፤ ወንጀለኞችንም ተከታትሎ በመያዝ ዞኑ ሰላማዊ እንዲኾን በርካታ ሥራዎች ተሠርተዋል ብለዋል።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ሙላት ማሞ የጸጥታ መዋቅሩ  ለኅብረተሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት እና የሕዝቡን ሰላም እና ደኅንነት በመጠበቅ ረገድ ያከናወናቸው ተግባራት በጥልቀት መገምገማቸውን ተናግረዋል።

ኅብረተሰቡ የጸጥታ ኀይሉን በመደገፉ ምክንያት የዞኑ ሰላም እና ደኅንነት የተረጋገጠ መኾኑን ነው የገለጹት።  ተሳትፎውን በማጠናከር የሕዝቡን ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጤንነት ማስጠበቅ እንደሚገባም ገልጸዋል።

ዞኑ ኤርትራን እና ሱዳንን የሚያዋስን በመኾኑ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታው ሀገራዊ ስለኾነ ጠንካራ የጸጥታ መዋቅር እንደሚያስፈልግ ታውቆ እየተሠራበት ነው ብለዋል።

የውስጥ እና የውጭ ኀይሎች የቦታውን ወሳኝነት በመረዳት ያልተገባ እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ ዞኑ የጸጥታ መዋቅሩን በንቃት ስምሪት እየሰጠ ነው ብለዋል። በመደራጀት ፣ በመተሳሰብ እና በመደጋገፍ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማጽናት እንደሚገባም አሳስበዋል።

የአውራ ወረዳ አሥተዳዳሪ ፈረደ በሪሁን የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት ለመጠበቅ የማይሰለች የጸጥታ መዋቅር መኖሩን ተናግረዋለ ሲል የዘገበው የአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን ነው።

Amhara Police Commission

11 Feb, 05:28


የደሴ ከተማ ፖሊስ ባደረገው ፍተሻ በህገ ወጥ መንገድ የተከማቸ ቤንዚን ከነ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር አውሏል።

ከህዝብ በተሰጠ ጥቆማና ክትትል ኮድ 1_ አማ የሴሌዳ ቁጥር 49738 በሆነ የባለ ሶስት ጎማ ባጃጅ ተሽከርካሪ ከኮምቦልቻ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ 210 ሊትር ቤንዚን ሲያጓጉዝ በኬላ ፍተሻ የተያዘ ሲሆን ይህንን ተከትሎ በተደረገ ምርመራ በደሴ ከተማ ዳንደቦሩ አካባቢ ኮንቲነር ውሰጥ ተደብቆ የነበረውን 356 ሊትር ቤንዚን ከ3 ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራው እየተጣራ ይገኛል።
በነዳጅ ምርቶች ላይ እየተከናወነ ያለውን ሸፍጥና ህገ ወጥ እንቅስቃሴ ለመከለል በትብብር መስራት እንደሚገባ የደሴ ከተማ ፖሊስ አሳስቧል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የካቲት 3/2017 ዓ.ም ምሽት ላይ አንድ ግለሠብ በሬ ሸጦ ወደ መኖራያ አድራሻው ለመመለስ የሚጓዝበትን ተሽከርካሪ ለማግኘት በሚጠብቅበት ሂደት ከኪሱ 20 ሺ ብር ሊወሰድበት ሲል ከነተጠርጣሪው በመናሀሪያው ውስጥ ስራ ላይ በነበሩት ፓሊሶች እጅ ከፈንጅ መያዙን የደሴ ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ አስታውቋል።

Amhara Police Commission

10 Feb, 09:22


"ተቋማት በቅንጅት በመሥራት የሕዝብን ችግር መፍታት አለባቸው" አቶ ደሳለኝ ጣሰው

የአማራ ክልል የአሥተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ተቋማት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ እና ውይይት እየተካሄደ ነው።

በውይይቱ ላይ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአሥተዳደር ጉዳዮች አስተባባሪ እና የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ኀላፊ ደሳለኝ ጣሰው እና ሁሉም የዘርፉ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።

በመድረኩ መክፈቻ ላይ መልእክት ያስተላለፉት አቶ ደሳለኝ ጣሰው የአሥተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ተቋማት አመራሮች እና አጠቃላይ የሥራ አባላት በክልሉ ሰላም እንዲሰፍን፣ የታቀዱ የልማት ሥራዎችም እንዲፈጸሙ ለማስቻል ሲተጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል። በተለይም የክልሉ ሕዝብ ሰላም እንዲረጋገጥ እና የተጋረጠበትን አደጋ ለመቀልበስ አስፈላጊውን ሁሉ መስዕዋትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ተቋማትን የያዘ ዘርፍ ስለመኾኑም ተናግረዋል።

አቶ ደሳለኝ በክልሉ ሰላም እና መልካም አሥተዳደርን ለማስፈን ሲሉ ዋጋ ሲከፍሉ ለቆዩ አመራሮች እና ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል።

የአሥተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ተቋማት ብልሹ አሠራሮችን ለማስወገድ እና በሕዝባችን ላይ የሚደርስ ሰቆቃ እና ምሬትን ቅርብ ኾነው የሚፈቱ ናቸው ብለዋል። በመኾኑም በሁሉም ተቋማት ልዩ የትኩረት አቅጣጫ ተቀምጦ ተግባራዊ ሥራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል ነው ያሉት።

እንደ ክልል የተፈጠረውን የሰላም እጦት በዘላቂነት ለመፍታት የአቅም ግንባታ እና የመፈጸም ብቃትን ማሳደግ ዋነኛ ተግባር እንደ ነበርም ተናግረዋል። ሕዝብን ለማገልገል የተዘረጉ ተቋማትን የሚመሩ አካላትን የመፈጸም አቅም በማብቃት አገልጋይነትን ከፍ ማድረግም የትኩረት አቅጣጫ ነበርም ብለዋል።

የመልካም አሥተዳደር ሥራዎችን በቁርጠኝነት በማከናወን ሕዝብ የሚተማመንበት ተቋም ለመገንባትም ሲሠራ ቆይቷል ነው ያሉት።

በቀጣይም ሕዝብን የሚያማርሩ አገልግሎት አሰጣጦችን በማረም፣ አገልጋይነትን የበለጠ በማሳደግ እና የሕዝብን እርካታ በማሳደግ ሕዝብ የሚተማመንባቸው ተቋማትን መፍጠር ግድ እንደሚል አሳስበዋል።

በሁሉም ተቋማት አዳዲስ ለውጦችን መተግበር እንደሚገባም አሳስበዋል። የሚፈጠሩ ለውጦች ከቆዩ ችግሮች የሚያላቅቁ፣ ዘመኑን የዋጁ፣ ፈጣን እና ሕዝብን ለማገልገል የተመቹ መኾን አለባቸው ብለዋል።

ተቋማት የተሻለ ለውጥ ያመጡ ዘንድ የተሻለ ቅንጅታዊ አሠራር መዘርጋት እንደሚያስፈልግም አቶ ደሳለኝ ጠቁመዋል። ለሕዝቡ ተደራሽ የኾነ የፍትሕ ሥርዓት ለመገንባት ጠንካራ የፖሊስ ተቋም መገንባት እና የምርመራ አቅምን ማሳደግ ይጠይቃል፤ ለዚህም በትብብር መሥራት ግድ ይላል ነው ያሉት።

"የተቀበልነው ሕዝባዊ ኀላፊነት ትልቅ መኾኑን በመረዳት አንዱ ተቋም ከሌላው ተቋም በመቀናጀት የሕዝብን ችግር መፍታት መቻል አለብን" ሲሉም አሳስበዋል።

በዛሬው የግምገማ እና ውይይት መድረክ ላይ በአሥተዳደር ጉዳዮች ዘርፍ ውስጥ የሚገኙ ተቋማት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸማቸውን አቅርበው ያስገመግማሉ። ከውይይቶች በኋላም ቀጣይ አቅጣጫዎች እንደሚቀመጡ ተጠቁሟል።

Amhara Police Commission

10 Feb, 08:33


የመንግሥትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ወጣቶች ለተሐድሶ ሥልጠና ወደ ስልጠና ማዕከል ገቡ።

አማራ ፖሊስ : የካቲት 03/2017 ዓ.ም

የመንግሥትን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ ወጣቶች ለተሐድሶ ሥልጠና ወደ ጠዳ የሥልጠና ማዕከል ገብተዋል።

ሠልጣኞቹ ለታጣቂዎች መረጃ በመሥጠት፤ ሎጅስቲክ በማቅረብ እና ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ መኾናቸው ተነስቷል።

የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ተስፋ መኮንን በክልሉ የተፈጠረው የጸጥታ ችግር ምክንያት ማኅበረሰቡ ከቦታ ቦታ እንዳይንቀሳቀስ እና ሠርቶ እንዳይበላ ጫና አሳድሯል ብለዋል።

በመነጋገር እና በመወያየት ችግሮችን ልንፈታ ይገባል ያሉት ኀላፊው ከግጭት ይልቅ የሰላም አማራጭን በመውሰድ ለክልሉ ሰላም ትልቁን ድርሻ ልትወስዱ ይገባል ነው ያሉት።

አንድነትን በማስቀደም አባቶች በመስዋዕትነት ያስረከቡንን ሀገር ሰላምን በማጽናት ለቀጣይ ትውልድ ልታስተላልፉ ይገባል ብለዋል። ሥልጠናውን በትኩረት በመውሰድ ከሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀትና ልምድ በመጠቀም ስለ ሰላም ሊሠሩ እንደሚገባም አሳስበዋል።
#አሚኮ

Amhara Police Commission

10 Feb, 04:50


በትራፊክ አደጋ 12 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደረሰ።

በደሴ ከተማ አስተዳደር ሰኞ ገበያ ክ/ከተማ ገራዶ 016 ቀበሌ ልዩ ቦታው አጋላ ከሚባለው ችግኝ ጣቢያ አካባቢ በቀን የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ/ም ከቀኑ 10:30 አካባቢ ከመካነ ሰላም ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ ኮድ3- ታርጋ ቁጥሩ 20637 የሆነ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ በመገልበጡ 4 ሰዎች ላይ ከባድ እና 8 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት አድርሷል።

ተጎጂዎች በደሴ ሪፈራል ሆስፒታል በህክምና ላይ ሲሆኑ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑን በደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ3ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ አደጋ መርማሪ ባለሙያ ዋ/ሳጅን ኤርሚያስ እያሱ ገልጸዋል ሲል የከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ ዘግቧል።

Amhara Police Commission

04 Feb, 13:23


የክልሉን ሰላም በዘላቂነት ለመፍታት በቁርጠኝነት መሥራት እንደሚገባ የቋሚ ኮሚቴ አባላት አሳሰቡ።

አማራ ፖሊስ: ጥር 27/2017 ዓ.ም

የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕ እና አሥተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚከታተላቸውን ተቋማት የሥራ አፈጻጸም እየገመገመ ነው።

ቋሚ ኮሚቴው የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ እና የተጠሪ ተቋማቱን የሥራ አፈጻጸም ገምግሟል።

የቋሚ ኮሚቴ አባላትም የጸጥታ ተቋሙ የክልሉን ሰላም ለማረጋገጥ እየከፈለው ያለው መስዋዕትነት ክብር የሚያሰጠው መኾኑን ገልጸዋል። በራስ አቅም የአካባቢን ሰላም ለማረጋገጥ እየተሠራ ያለው ሥራም የሚበረታታ ነው ብለዋል።

መስዋዕትነት እየከፈለ በሠራው ሥራ በክልሉ አንጻራዊ ሰላም እንዲመጣ አድርጓል ነው ያሉት። የጸጥታ ኀይሉ ለሕዝብ ሰላም እና ደኅንነት በጀግንነት እየታገለ ነው፣ ለዚህ ክብር ልንሰጠው ይገባል ብለዋል።

የጸጥታ ችግሩን ሕግ በማስከበር ብቻ ሳይኾን በእርቅ እና በይቅርታ ለመፍታት እየተሄደ ያለው ርቀትም የሚበረታታ ነው ብለዋል።

የጸጥታ ተቋሙ የክልሉን የጸጥታ ችግር በዘላቂነት ለመመለስ መስዋዕትነት ከመክፈል ባሻገር ውይይትን እንደ አማራጭ መጠቀም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ነው ያሉት።

ከሕዝብ ጋር ጥብቅ ቁርኝት መፍጠር እንደሚጠበቅበትም አንስተዋል። የክልሉን ግጭት በውይይት እና በሰላማዊ መንገድ በመቋጨት ሕዝቡን ከተራዘመ ጦርነት መውጣት ይጠበቃል ነው ያሉት።

የሰላም እና የጸጥታ ተቋማት የሕዝብን መታገት፣ መገደል እና መጎዳት ማስተካከል እንደሚገባቸውም ገልጸዋል። የጸጥታ ኀይሉን መፈተሽ እና ታማኝነቱን ማረጋገጥ እንደሚገባ ነው የተናገሩት።

ለሕዝብ የሚሠሩ እንዳሉ ሁሉ መረጃ የሚያወጡ ከመንግሥት በተቃራኒ የሚሠሩ የጸጥታ ኀይሎች አሉ ነው ያሉት።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/share/p/19qZHk8Zts/

Amhara Police Commission

04 Feb, 13:13


በወረታ ከተማ በተደረገ ኦፕሬሽን ውጤታማ ተግባር መከናወኑን የወረታ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታወቀ።

በወረታ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኘው ቋሃር ሚካኤል በተባለ የገጠር ቀበሌ ውስጥ በዛሬው ዕለት ማለትም ጥር 27/2017 ዓ.ም እረፋድ ላይ በነበረው የሰላም ማስከበር ኦኘሬሽን በፅንፈኛው ላይ የተሳካ ኦፕሬሽን መደረጉን የወረታ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት አስታውቋል።

የመንግስት ታጣቂ ኃይሎች በወሰዱት የጸጥታ ማስከበር ኦኘሬሽን እርምጃ ላይ 5 የፅንፈኛ ቡድን መደምሰሱንና 8 የጠላት ቡድን ደግሞ መቁሰሉን እንዲሁም 1 ብሬንና 4 ክላሽ የጦር መሣሪያዎች መማረካቸውን ጽ/ቤቱ ገልጿል።

በተደረገው ኦኘሬሽን ላይ ከመንግስት ጸጥታ አስከባሪና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ምንም አይነት ጉዳት አለመድረሱንና ይህም ድል የተገኘው በተደራጀና በተቀናጀ የመረጃ መዋቅር ፣በወረታ ከተማ አስተዳደር ጸጥታ አስከባሪ ኃይሎችና አድማ ብተና እንዲሁም በፎገራ ወረዳ አጋዥ አድማ ብተናና የጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት መሆኑን በጽ/ቤቱ ጨምሮ ገልጿል።

መረጃው፦የወረታ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬን ነው።

Amhara Police Commission

03 Feb, 18:47


"ለፍትህ ስርዓቱ ውጤታማነት በትብብር መስራት ይገባል"
ምክትል ኮሚሽነርና የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረ/ኮሚሽነር ውበቱ አለ
አማራ ፖሊስ፡ጥር/2017 ዓ.ም

የአማራ ክልል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ የሰድስት ወራት አፈፃፀምን በገመገመበት ወቅት ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ወንጀል ምርመራ ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ውበቱ አለ በዘንድሮው ግማሽ ዓመት በተፈለገው አግባብ ተንቀሳቅሶ ለመስራት እንቅፋቶች ቢኖሩም በብዙ ችግሮች ውስጥ ሆኖ በግማሽ ዓመቱ ከቀረቡ 5453 መዝገቦች 4725ቱ ተጣርተው ለዐቃቤ ህግ ተልከዋል። ይህም የምርመራ የማጣራት ዐቅምን 86.9 በመቶ ያደርሰዋል ብለዋል።
ምንም እንኳን ወቅቱ ፈታኝ ቢሆንም በተፋጠነ የፍትህ ስርዓት መታዬት ከነበረባቸው 1108 መዝገቦች 956ቱን በማቅረብ 86.4 በመቶ መፈፀምም ተችሏል።

በወንጀል ምርመራ ዘርፍ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ም/ዘርፍ ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር ክንዱ ወንዴ በበኩላቸው የነበሩንን ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለዬት ድክመቶቻችንን አርመን የቀጣይ አቅጣጫ ማስቀመጥ ይኖርብናል ብለዋል።

Amhara Police Commission

03 Feb, 13:28


የሕዝብን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችል ወታደራዊ ሥልጠናዎችን መውሰዳቸውን የፍኖተ ሰላም ተመራቂ ሚሊሻዎች ተናገሩ።

አማራ ፖሊስ: ጥር 26/2017 ዓ.ም

በፍኖተ ሰላም ማዕከል ሥልጠናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የፍኖተ ሰላም ቀጣና የ2ኛ ዙር የሰላም አስከባሪ እና የሚሊሻ አባላት የምረቃ ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።

ተመራቂዎቹ የአካባቢያቸውን ሰላም እና ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችል አካላዊ እና ወታደራዊ ሥልጠናዎችን በሚገባ ስለመውሰዳቸው በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የመከላከያ ሠራዊት የሰላም ማስከበር ማዕከል ኀላፊ ሜጀር ጀኔራል አዳምነህ መንግስቴን ጨምሮ የዞን እና የፍኖተ ሰላም ከተማ አሥተዳደር መሪዎች ተገኝተዋል።

Amhara Police Commission

03 Feb, 13:11


‘’የጸጥታ መዋቅሩን እና የኅብረተሰቡን አቅም አቀናጅቶ በመጠቀም ዘላቂ ሰላም የማፅናት ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል’’ የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር

አማራ ፖሊስ፦ ጥር 26/2017 ዓ/ም
የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ የ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት ሕግ የማስከበር ሥራ አፈፃፀም እና የቀጣይ አቅጣጫዎችን ገምግሟል። ከሁሉም ወረዳዎች እና ከተማ አሥተዳደሮች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ነው ግምገማው የተካሄደው።

በግምገማ መድረኩ የተገኙት የአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ምክትል አሥተዳዳሪ እና የከተማ እና መሠረተ ልማት መምሪያ ኀላፊ አይተነው ታዴ እንደ ክልል የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ በርካታ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ማስከተሉን ተናግረዋል።

የጸጥታ መዋቅሩ በጠንካራ ሕዝባዊ ድጋፍ ታጅቦ በከፈለው መስዋዕትነት የብሔረሰብ አሥተዳደሩ አብዛኛዎቹ አካባቢዎች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው መመለሳቸውንም ምክትል አሥተዳዳሪው ገልጸዋል።

የፀጥታ መዋቅሩን እና የኅብረተሰቡን አቅም አቀናጅቶ በመጠቀም የብሔረሰብ አሥተዳደሩን ዘላቂ ሰላም የማፅናት ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ምክትል አሥተዳዳሪው አንስተዋል።

የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ጌታቸው ቢሻው የሕይዎት እና የአካል መስዋዕትነት ተከፍሎበት የተገኘው ሰላም እንዳይቀለበስ ዘላቂ ሰላምን የማስፈን ሥራ ሕዝባዊ መሠረት እንዲኖረው እየተሠራ መኾኑን ተናግረዋል።

በብሔረሰብ አሥተዳዳሩ አሁን እየመጣ ላለው ሰላም የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የኅብረተሰቡ ሚና የጎላ እንደኾነም ኀላፊው አንስተዋል።

የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ከጸጥታ መዋቅሩ ጋር በቅንጅት በሠሩት ሥራ በብሔረሰብ አሥተዳደሩ ከ240 በላይ የታጠቁ ኀይሎች የመንግሥት እና ሕዝብ የሰላም ጥሪን ተቀብለው ወደ ማኅበረሰቡ ተቀላቅለዋልም ነው ያሉት።

የብሔረሰብ አሥተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር እሱባለው መኮንን በበኩላቸው ለሕገ መንግሥቱ እና ለሕዝብ ዘብ የቆመ የጸጥታ መዋቅር በመገንባት ሕግ የማስከበር ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

Amhara Police Commission

03 Feb, 13:06


በፀጥታው ችግር ምክንያት ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ የሴቶችን የመደገፍ ስራ እየተሰራ መሆኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ገለፀ።

የምዕራብ ጎጃም ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ የሴቶች የተደራጀ እና ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ልማት ግንባታ በሚል መሪ ቃል ከሴት የመንግስት ሰራተኞች ጋር የውይይት መድረክ በፍኖተ ሰላም ከተማ አካሂዷል።

መድረኩ ላይ የተገኙ በምዕራብ ጎጃም ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ኀላፊ አቶ ሙላት ጌታቸው በክልሉ የገጠመውን የሰላም እጦት በኢኮኖሚ ፣ በፓለቲካ እና ማህበራዊ ዘርፎች በርካታ ቀውሶች እያደረሰ መኾኑን ተናግረዋል።

ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት የመጀመሪያ ተጠቂዎች ሴቶች መኾናቸውን ገልፀው ለሰላም ግንባታ የሴቶች ሚና የጎላ በመኾኑ የበኩላቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።

ሴቶች በማህበራዊ ፣ በፓለቲካዊ እና ኢኮኖሚ ውስጥ ያላቸው ተሳትፎ ወሳኝ በመሆኑ ሰላምን ለመጠበቅ እና ለማሳደግ አይነተኛ አበርክቶ አለው ።

በፀጥታው ችግር ምክንያት ለጥቃት ተጋላጭ የሆኑ የሴቶች ማህበራትን በማስተባበር የመደገፍ ስራ እየተሰራ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያ ኀላፊ ስለእናት ዘሪሁን ተናግረዋል ።

በተለይም የሴት አደረጃጀቶችን በማጠናከር ሴቶች ለሰላም ግንባታ የበኩላቸውን እንዲወጡ እየተደረገ መሆኑን ገልፀው ፤ ታጥቀው ወደ ጫካ የገቡ ኃይሎችም ፊታቸውን ወደ ሰላም እንዲያዞሩ ነው ወ/ሮ ስለእናት የጠየቁት።

ሴቶች በማህበራዊ ፣ ፓለቲካ እና ኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱ ሁሉ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የሰላም ግንባታ ሂደት ላይ ተሳትፏቸውን የማጠናከር ስራ እየተከናወነ መኾኑን የምዕራብ ጎጃም ዞን ሴቶች ሊግ ኀላፊ ወ/ሮ አክሊለ ዞማነህ ገልፀዋል።

በውይይት መድረኩ ላይ የተሳተፉ ሴት የመንግስት ሰራተኞችም የፀጥታ ችግሩ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ቅድሚያ በመስጠት እና ከዚህ የከፋ ችግር ሳይከሰት ሁሉም አካላት ለውይይት እና ለድርድር ዝግጁ መሆን አለባቸው ለዚህ ደግሞ ሁሉም ማህበረሰብ ሊረባረብ ይገባል ነው ያሉት።

Amhara Police Commission

03 Feb, 05:19


13 ታጋቾች እንዲለቀቁ ተደረገ።

13 ታጋቾችን ከእገታ ማስለቀቁን የጭልጋ ወረዳ ሰላም እና ደህንነት ጽሐፈት ቤት አስታውቋል።

መነሻውን አዘዞ አድርጎ ወደ መተማ እየሄደ ባለ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ተሳፍረው ከነበሩት ተሳፋሪዎች 13ቱ ታግተው እንደነበር ተገልጿል።

የጭልጋ ወረዳ ሰላም እና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት ምክትል ኀላፊ መላኩ አብዬ የጭልጋ ወረዳ የጸጥታ ኃይል በደረሰው መረጃ ወደ ቦታው በመግባት ባደረገው የተኩስ ልውውጥ 13ቱን ታጋቾች ማስለቀቁን ተናግረዋል።

መንገድ ላይ እየተደረገ ያለው እገታ ማኅበረሰባችን ጉዳት ላይ የሚጥል ነው ያሉት ምክትል ኀላፊው ማኅበረሰቡ መረጃ በመስጠት ከጸጥታ ኀይሉ ጋር እንዲሠራ አሳስበዋል።

የጭልጋ ወረዳ ሚሊሻ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ጋሻው ብርሀኔ እገታ የማኅበረሰቡን ኢኮኖሚ ከመጉዳት ባሻገር በሥነ ልቡና ላይም ትልቅ ተፅእኖ እንደሚያሳድር ተናግረዋል።

ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል የእገታ ተግባርን በማውገዝ እና መረጃ በመስጠት ከጸጥታ መዋቅሩ ጎን እንዲሰለፍ ጠይቀዋል።

ከማዕከላዊ ጎንደር ዞን ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ከእገታ የተለቀቁ ወገኖች በሕይወታቸው ለደረሰላቸው የወረዳው የጸጥታ ኀይል ምስጋና አቅርበዋል።

እገታን ሁሉም ማኅበረሰብ ሊያወግዘው እና ሊከላከለው የሚገባ ተግባር መኾኑንም ተናግረዋል።

Amhara Police Commission

01 Feb, 16:21


የ6 ዓመት ህፃን ያገተ ግለሰብ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።

ህፃን ኢብራሂም ጀማል የሱፍ ዕድሜው 6 ዓመት ሲሆን በደ/ወሎ ዞን ወራኢሉ ወረዳ ቀበሌ 01 ጥር 23 /2017 ዓ/ም ከቀኑ 5:00 ሰዓት ገደማ የጠፋ መሆኑን ወላጅ አባቱ አቶ ጀማል የሡፍ ገልፀዋል።

የህፃኑ አባት ልጁ መጥፋቱን እንዳረጋገጡ በጠፋ ከ5 ሰዓታት በኋላ ማለትም ጥር 23/2017 ዓ/ም ከቀኑ 10 ሰዓት ገደማ በኮምቦልቻ ከተማ ለአቢሻገር ክ/ከተማ ፖሊስ እንዳሳወቁ ተመላክቷል።

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የአቢሻገር ክ/ከተማ ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ም/ኢ/ር ሁሴን መብራቱ እንዳሉት የእግታ ወንጀሉ መረጃ እንደደረሰ ፖሊስ በኬላና በሁሉም አጠራጣሪ ቦታዎች ጥብቅ ክትትል ሲያደረግ እንደነበር ገልፀዋል።

ሀላፊውም እንዳሉት ከተጠናከረ ክትትልና ፍተሻ በኋላ በ2ኛው ቀን ጥር 24/2017 ዓ/ም ከጧቱ 2 ሰዓት በኬላ ፍተኛ ህፃኑን ከአጋች ሰይድ ኡመር ጣሂር ጋር በቁጥጥር ስር እንዳዋሉ እና ህፃኑን ከነ ሙሉ ጤንነቱ ለወላጅ አባቱ ያስረከቡ መሆኑን አስረድተዋል።

እንደ ኢንስፔክተሩ ገለፃ በአጋቹ ላይ ምርመራ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

ያነጋገርናቸው የታጋች ህፃን አባት አቶ ጀማል የሱፍ ልጃቸውን በማግኘታቸው ደስታቸው እጥፍ መሆኑን ገልፀው ልጃቸውን የታደገላቸውን ፖሊስ ታላቅ የሆነ አክብሮትና ምስጋና ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የአቢሻገር ክ/ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኢ/ር ሁሴን መብራቱ እንዳሉት ለፖሊስ ሀይሉ የሚሰወር የወንጀል ድርጊት አይኖርም ማህበረሰቡ በአካባቢያቸው ፀጉረ ልውጥ እና አጠራጣሪ ሰዎች ሲያጋጥም ለፖሊስ ጥቆማ መሥጠት፤ ራሥን፣ ቤተሰብን እና ንብረትን መጠበቅ እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

በጀግንነት መጠበቅ በሰባዊነት ማገልገል!!

#መረጃው በኮምቦልቻ ከተማ የአቢሻገር ክፍለ ከተማ ፖሊስ ነው።

Amhara Police Commission

01 Feb, 11:44


የሰላም ጥሪን የተቀበሉ የታጠቁ አካላት ወደ ሕዝብ እና መንግሥት ተመለሱ።

አማራ ፖሊስ: ጥር 24/2017 ዓ.ም
በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ በሕዝብ እና በመንግሥት በተደጋጋሚ ይቀርብ የነበረውን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የታጠቁ አካላት በሰላም መግባታቸውን የወረዳው አሥተዳደር አስታውቋል።

በደቡብ ወሎ ዞን በተሁለደሬ ወረዳ 027 ሙጢበልግ እየተባለ በሚጠራው ቀበሌ በተሳሳተ መንገድ ነፍጥ አንግበው የነበሩ አካላት ናቸው የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ሕዝብ እና መንግሥት የተመለሱት።

የታጠቁት አካላት ወደ አካባቢያቸው ሲደርሱ በተሁለደሬ ወረዳ የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የተሁለደሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ደመቁ አበበ፣ የመከላከያ ሠራዊት መሪዎች፣ ሌሎች የወረዳው የሥራ ኀላፊዎች፣ የጸጥታ መዋቅር መሪዎች፣ የአካባቢው የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት አቀባበል ስለመደረጉ ከደቡብ ወሎ ዞን የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#አሚኮ

Amhara Police Commission

01 Feb, 08:20


"ማኅበረሰቡ ፍፁም የሰላም አየር አስኪተነፍስ ድረስ ሕግ የማስከበር ሥራው ተጠናክሮ ይቀጥላል" የምዕራብ ጎጃም ዞን

አማራ ፖሊስ : ጥር 24/2017 ዓ.ም
የምዕራብ ጎጃም ዞን የሥድስት ወራት የሕግ ማስከበር የሥራ አፈፃፀም ግምገማ እያካሄደ ነው።

በግምገማ መድረኩ ላይ የተገኙት በምዕራብ ጎጃም ዞን ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፓለቲካ ዘርፍ ኀላፊ ሙላት ጌታቸው በክልሉ ባጋጠመው የሰላም እጦት የክልል እና የፌዴራል የጸጥታ አካላት በከፈሉት መሰዋዕትነት አንፃራዊ ሰላም መገኘቱን ተናግረዋል።

ባለው የሰላም እጦት ማኅበረሰቡ ለከፍተኛ ችግር መጋለጡን አንስተው ማኅበረሰቡ ፍፁም የሰላም አየር አስኪተነፍስ ድረስ ሕግ የማስከበር ሥራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው አቶ ሙላት የገለጹት።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኀላፊ ሙሉጌታ ዓለም የጸጥታ ችግሩን ለመፍታት የጸጥታ ኀይሉን ማጠናከር ወሳኝ በመኾኑ ባለፉት ሥድስት ወራት የሰላም አስከባሪ እና የሚኒሻ ኀይል በማደራጀት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ነው ያስገነዘቡት።

#አሚኮ

Amhara Police Commission

01 Feb, 07:50


የአገው ፈረሰኞች በዓል በሰላም ተጠናቋል።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/share/p/1A71wzrLXX/

Amhara Police Commission

01 Feb, 07:21


በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ክልላዊ የ2017 ዓ/ም 6 ወር የእቅድ አፈፃፀም ግምገማና የውይይት መድረክ ተካሄደ።

አማራ ፖሊስ፦ጥር 24/2017 ዓ.ም
ክልሉ ለወራት የሰላም መደፍረስ የነበር ቢሆንም ከጊዜ ወደ ጊዜ ሰላም እየተረጋገጠ የመጣበት ሁኔታ አለ ተብሏል።

በመድረኩ የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀብታሙ ሲሳይ፣ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ም/ኮሚሸን ረዳት ኮሚሸነር እንየው ዘውዴ፣የኮምቦልቻ ከተማ አስ/ር ም/ከንቲባ ወንድወሰን ልሳነወርቅ፣ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ኮ/ር ሳይድ አሊ፣ የፖሊስ መምሪያ ሀላፊ ኮ/ር ጌታቸው ሙህዬ፣ የሚኒሻ ጽ/ቤት እና የማረሚያ ቤት የስራ ኃላፊዎችና የማኔጅመንት አባላትም ተገኝተዋል ።

በዕቅድ አፈፃፀሙ ላይ በዋናነት በክልሉ ሰላም አለመኖርን ተከትሎ የነበሩ የሰውና የንብረት ውድመቶችን ተመላክቷል።

ለዚህም በሀገር መከላከያና የክልሉ የፀጥታ መዋቅሮች የጋራ ተጋድሎ በክልሉ የተንሰራራውን የጽንፈኛ ቡድን መበተን የተቻለ ሲሆን በቀጣይ ሰላም እንዲፈጠር የበለጠ ርብርብና የህብረተሰብ ድጋፍ ያሸዋል ተብሏል።

በክልሉ መንግስት በኩል ለፀጥታ ሀይሉ የሚያስፈልጉ ሁለንተናዊ ድጋፎች እንደሚደረግም ተገልጿል።

በጀግንነት መጠበቅ በሠባዊነት ማገልገል!

Amhara Police Commission

31 Jan, 12:04


❝ብዝሃ ማንነት ባለበት ሀሳቦችና ልዩነቶች መኖራቸው አይቀሩም ልዩነቶች እና አለመግባባቶች በሰፊ አስተውሎት መፍታት የዘመኑ መጣኝ ገድል ነው።❞
አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ።

"አርበኝነታችን ለአሁናዊ ሰላማችን"በሚል መሪ ቃል 85ኛው የአገው ፈረሰኞች ቀን በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በእንጅባራ ከተማ በድምቀት ተከብሯል።

በዕለቱ የተገኙት የብሄረሰብ አስተዳደሩ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው እንደገለፁት አገራችን የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች በጋራ የሚኖሩባት ብዝሃ ቋንቋ እና ብዝሃ ልዩነቶች መናገሻ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ የሚኖሩ የሀሳብ ልዩነቶች የግጭት መንስኤዎች ሊሆኑ አይገባም ብለዋል።

የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች አንዳችን ለአንዳችን በመደጋገፍ የቆምንባት ታሪካዊት ሀገር ባለቤቶች ነን የፅንፈኝነት እና ጎጠኝነት አስተሳሰብ ሊያጋጨንም ሆነ ሊያለያየን አይገባም።

ሰላም የዋጋ ተመን የማይበጅለት፣የሰው ልጅ መሰረታዊ ፍላጎቱን ተጠቅሞ ለመኖር ዋስትናና ማረጋገጫ ሰነድ ነው።የክልላችን ህዝብ የራሱን እኩይ ተግባር በሚያራምድ የአብራኩ ክፋይ የመከራ ዋጋ እየከፈለ ነው ብለዋል ዋና አስተዳዳሪው።

የእልህ ፖለቲካ ኪሳራው ዘርፈ ብዙ ነውና የህዝባችንን ምሬትና ሰላም ናፋቂነትን ልብ በማለት ወደ አሳደጋችሁ ማህበረሰብ በመቀላቀል የተረጋጋና በልማቱ ተጠቃሚ የሆነ ማህበረሰብ እንዲንፈጥር ለሰላማችን እንትጋ ሲሉ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው ጫካ ለገቡ ታጣቂዎች መልዕክት አስተላልፈዋል።

Amhara Police Commission

31 Jan, 07:46


"ለሰላም መረጋገጥ እና ለማህበረሰብ ደህንነት የማይተጉ እጆች አይኖሩንም።"
ኮሚሽነር ደስየ ደጀን_ የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር

አማራ ፖሊስ፦ጥር 23/2017 ዓ.ም
የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ባለፉት 6 ወራት በተከናወኑ የህግ ማስከበር እና ሰላም የማስፈን እንዲሁም በቀጣይ ሰላም በማስፈን ተግባር በሚደረጉ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ግምገማና ምክክር ያደረገ ሲሆን በዚህም የክልሉን ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደስየ ደጀንን ጨምሮ የክልልና የከተማ ፖሊስ አመራሮችና ሌሎች የፀጥታ ዘርፉ አስተባባሪዎች ተገኝተዋል።

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.facebook.com/share/p/19rMnHqojf/

Amhara Police Commission

30 Jan, 11:54


ለሰላም ግንባታ የኅብረተሰቡ ሚና” በሚል መሪ ሃሳብ በደሴ ከተማ በክ/ከተማ ደረጃ የመንግሥት ሰራተኞች የሰላም ዉይይት ተካሄደ።

በደሴ ከተማ አስተዳደር በክ/ከተማ ደረጃ የሚገኙ የመንግሥት ሰራተኞች “ለሰላም ግንባታ የኅብረተሰቡ ሚና” በሚል ሃሳብ የሰላም ዉይይት አካሂደዋል።

ሰላምን ለማፅናት በተለይም የመንግሥት ሰራተኛዉ ማኅብረሰብ ስለ ሰላም ማወቅና የሰላም ግንባታን ባህል ማድረግ መቻል እንዳለበት የተገለፀ ሲሆን የሰላም ባህል በውጫዊ ብዝኃነት ላይ የተመሰረተ ሰብዓዊነትና የአዲስ ሥልጣኔ ፍሬ ተደርጐ ሊታይ የሚገባው ተግባር መሆኑ ተወስቷል።

ደሴ ከተማ የሰላም ተምሳሌትነቷን ለማስጠበቅ፣ ለኑሮ ምቹና ተስማሚ እንድትሆን በማድረግና ከሰላም ሥራዉ ጎን ለጎን መንግሥት ሰራተኛዉ በመደበኛ የሥራ ገበታዉ ላይ በመገኘትና የአገልጋይነት መንፈስን በመላበስ ለኅብረተሰቡ የተቀላጠፈና የላቀ አገልግሎት መሥጠት እንዳለበት ተመላክቷል።

ሰላም የህልውና ጉዳይና የሀገር ዕድገት መሰረት በመሆኑ የመንግሥት ሰራተኞች እውነተኛ ሰላም ወዳድነታቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
መረጃ፦የደሴ ከተማ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።

Amhara Police Commission

13 Jan, 10:32


ህገ-ወጥ መድኃኒት ሲያዘዋውር የተገኘው ግለሰብ መቀጣቱን ፖሊስ ገለፀ።

ባህርዳር፦ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም (አማራ ፖሊስ ሚዲያ)
በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ሰሃላ ሰየምት ወረዳ 06 ቀበሌ ታኅሳስ 24 ቀን 2017 ዓ/ም አዲሡ አዳነ ወረታ የተባለ ግለሰብ አዳኝነቱና ፈዋሽነቱ ያልተረጋገጠ ህገወጥ መድሀኒት በ2011 የወጣውን የምግብና መዳኃኒት አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1112/2011 አንቀፅ 2/44/ እና አንቀፅ 67/4/ስር የተመለከተውን በመተላለፍ በህገወጥ መንገድ ለማዘዋወር ሲሞክር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል።

የወረዳው ፖሊስም ምርመራውን በማጣራት መዝገቡን ለወረዳው ዐቃቤ ህግ ጽ/ቤት ልኳል።

ክሱ የቀረበለት የስሃላ ሰየምት ወረዳ ፍርድ ቤትም በተፋጠነ የፍርድ ሂደት የግለሰቡን ጥፈትኝነ በማረጋገጥ ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት እሱን ያርማል ሌላውንም ያስተምራል ያለውን በ1ዓመት ከ8 ወር እስራት እና በ3,000(ሶስት ሽህ ) ብር የገንዘብ መቀጮ እንድቀጣ ወስኖበታል ሲል የሰሀላ ሰየምት ወረዳ ፖሊስ ዘግቧል።

Amhara Police Commission

12 Jan, 08:08


በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ወረዳ የሠላምን ጥሪ የተቀበሉ ታጣቂዎች እጅ ሠጥተዋል።

የሰሜን ጎንደር ዞን ኮማንድ ፖሰት ሰብሳቢ ሜጄር ጄኔራል አማረ ገብሩ እንደገለፁት በአካባቢው ታጥቀው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ እና በህብረተሰቡ ላይ ችግር ሲፈጥሩ የቆዩ ቡድኖች የመንግስትን የሠላም ጥሪ በመቀበል እጃቸውን እየሠጡ ይገኛሉ።

የመከላከያ ሠራዊቱ ከአካባቢው የፀጥታ ሀይል ጋር በመቀናጀት ባደረገው የሚያቋርጥ ስምሪት ቡድኑ ላይ ተከታታይ እርምጃ በመወሰዱ አካባቢው የሰላም ቀጠና ሊሆን መቻሉንም አሥረድተዋል።

ሠራዊቱን በማሰማራትና ጠላት እሰከሚሸሸግባቸው በርሃዎች ዘልቆ በመግባት በተወሰደው ተከታታይ እርምጃ አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ሜጄር ጄኔራል አማረ ገብሩ ገልፀዋል።

ህብረተሠቡም ለሰላም በመምከር በተሳሳተ አጀንዳ ወደ ታጣቂ ቡድን የተቀላቀሉት ወደ ሠላም እንዲመለሱ ሠፊ ሥራ መሥራቱን የገለፁት ጄኔራል መኮንኑ አሁንም በተሳሳተ መንገድ ጫካ የሚገኙትን መምከርና ወደ ሠላም መመለስ እንደሚገባ አመላክተዋል።

እጅ የሰጡት ታጣቂዎች የሰጡት ሃሳብ ከግጭት እና ከጦርነት የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ተገንዝበው የሠላም አማራጭን መቀበላቸው ለክልሉ ህዝብ ሠላም ያላቸውን ቁርጠኝነት ያመለክታል።

ወደ ሠላም የተመለሱ ታጣቂዎች በሀሰት ፕሮፖጋንዳ ተታለው ወደ ጫካ እንደገቡ ገልፀው ሲበድሉት የቆዩትን ህዝብ ለመካስ ከፀጥታ ሃይሉና ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት እንደሚሠሩ ተናግረዋል።

ምንጭ ፦የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት

Amhara Police Commission

11 Jan, 16:09


"በሴቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች በአብዛኛው በቤት ውስጥ በመሆኑ ከደረስንበት ይልቅ ያልታወቀው የበዛ ነው"
ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ_የሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኅላፊ

በአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የፀረ ፃታ ጥቃት ቀንን ለመዘከር በተሰናዳው መድረክ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ሴቶችና ህፃናት ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኀላፊ ወ/ሮ ብርቱካን ሲሳይ አንደኛው ችግር ሌላኛውን እየወለደ የሴቶችን ተጠቂነት አባብሶታል ብለዋል።
ስለ ስርዓተ ፆታ ያለው ግንዛቤ ባለመቀዬሩ ከጎጂዎች ይልቅ ተጎጂዎች የሚደበቁበትና የሚሸማቀቁበት አግባብ እየተፈጠረ መሆኑን ያነሱት ቢሮ ኀላፊዋ ፖሊስ ያለመገፋፋት መስራት ይኖርበታል። በተለይም በቤት ውስጥ የሚፈፀሙ ጥቃቶችን ከታወቀው ይልቅ ያልተደረሰበት ስለሚበልጥ ድርጊቱን ለማስቆም ፖሊስ የረቀቀ የምርመራ አቅምን ማሳደግ ይጠበቅበታል ብለዋል።

በአማራ ክልል የፍትህ ባለሙያዎች ማሰልጠኛና የህግ ምርምር ኢንስቲትዩት ተመራማሪና አሰልጣኝ የሆኑት ወ/ሮ አበባ ታደሰ ለመድረኩ ታዳሚዎች በሴቶችና ህፃናት ጥቃት ዙሪያ ፁሁፍ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት "የሴቶችን ጥቃት ለማስቆም የህግ አስከባሪዎችን ግንዛቤ ማሳደግ ይገባል"ብለዋል።

በተለያዩ ክስተቶች ቅድሚያ ተጋላጭ ከሚሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች መካከል ሴቶች፣ ሕፃናትና አካል ጉዳተኞች ናቸው የሚሉት ወ/ሮ አበባ ተጋላጭነታቸውን በመቀነስ የሚደርሱ ጥቃቶችን ለመከላከል እና የግንዛቤ ፈጠራ ሥራ ለመሥራት ቀኑ ታስቦ መዋሉ ጠቀሜታው የጎላ ሲሆን በተለይም ፖሊስ እንደተቋም የሴቶችን ጥቃት የመከላከልና የመጠበቅ ድርብርብ ኀላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

በግጭቶች እና በሌሎች ተያያዥ ችግሮች ምክንያት የሚፈፀሙ ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች መበራከታቸውን ስንመለከት ከቀን ማክበር በዘለለ ችግሩን ለመከላከል መተባበር እንዳለብን ያሳያል ብለዋል።

የሴቷ ጥቃት የኔም ነው፤ዝም አልልም !

Amhara Police Commission

11 Jan, 14:16


"የሴቶችን ጥቃት ለማስቆም የወንጀል መከላከልና ምርመራ ስራዎችን ማሻሻል አለብን" ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ33ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ19ኛ ጊዜ የተከበረውን የጸረ ፆታዊ ጥቃት ነጭ ሪቫን ቀን ምክንያት በማድረግ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ሰራተኞች ምክክር አድርገዋል።

"የሴቷ ጥቃት የኔ ነው፤ ዝም አልልም" በሚል መሪ መልዕክት በተከበረው በዚህ መርሀ ግብር ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሸን ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን ቀኑን ስናስብ በተለያዬ አጋጣሚ ፆታዊ ጥቃት የሚደርስባቸውን ሴቶች ለመጠበቅ ግንዛቤያችንን በማሳደግ መሆን አለበት ያሉት ኮሚሽነሩ ከገጠር እስከ ከተማ የሴቶች ጥቃት እየጨመረ መሆኑን ገልፀዋል።
በተለይም አሁን በገጠመን የፀጥታ ችግር ቀዳሚ ተጠቂ የሆኑትን ሴቶች ከፃታዊ ጥቃት እስከ ሀብት መነጠቅ ድረስ ባለው ሂደት ቅድሚያ ሰጥቶ በልዩ ትኩረት ለመጠበቅ የወንጀል ምርመራ ስራዎቻችንን ማሻሻል ይጠበቅብናል ብለዋል።

የፖሊስ ኮሚሽኑ ሴቶችና ህፃናት መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ሀገርነሽ ፀጋው በበኩላቸው በሴቶችና ህፃናት ላይ የሚደርሱ ወሲባዊ፣ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጉዳቶችን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት በትብብር መስራት አለብን ብለዋል።

በመድረኩ የተገኙ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በተለያዩ ክስተቶች ቅድሚያ ተጋላጭ ከሚሆኑ የማኅበረሰብ ክፍሎች መካከል ሴቶች፣ ሕፃናትና አካል ጉዳተኞች በመሆናቸው በልዩ ትኩረት ለመጠበቅ እንደሚሰሩ አረጋግጠዋል።

Amhara Police Commission

11 Jan, 13:26


የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ሞዴል የሴቶች የልማት ኅብረቶችን ለመፍጠር ያለመ የምክክር መድረክ በባሕር ዳር ከተማ አካሂዷል።

መድረኩ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት በአደረጃጀት መፍታት ላይ ያተኮረ ነው። ከዚህ በፊት የነበሩ የአደረጃጀት ክፍተቶችን አሻሽሎ አተገባበራቸው ላይ በአጽንኦት መሥራትንም ያለመ ነው።

በምክክር መድረኩ የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ፣ በአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካ እና ዓቅም ግንባታ ዘርፍ ኀላፊ ዘሪሁን ፍቅሩ (ዶ.ር)፣ የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኀላፊ ብርቱካን ሲሳይን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ተሳትፈዋል።

የውይይት መነሻ ጽሑፍ ያቀረቡት የሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ምክትል ኀላፊ ዝና ጌታቸው የመድረኩ ዓላማ በተለያዩ የልማት ዘርፎች ሞዴል የሴቶች ልማት ኅብረት ለመፍጠር ነው ብለዋል።

የልማት ኅብረቱ ሴቶች ተሞክሯቸውን በመለዋወጥ እና በመደጋገፍ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ወሳኝነት አለው ነው ያሉት።

ሴቶች በአትክልት እና ፍራፍሬ ልማት፣ በእንስሳት እርባታ፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ ዘርፎች እና ሌሎችንም ጸጋዎችን በመጠቀም ኑሯቸውን እንዲቀይሩ፣ የሚያጋጥማቸውን የበጀት፣ የግብዓት እና የሕግ አገልግሎት እጥረቶች እንዲፈቱ መታገዝ አለባቸው ብለዋል። ለዚህ ደግሞ ጠንካራ አደረጃጀቶች ሊፈጠሩ እንደሚገባ ነው ያብራሩት።

የአማራ ክልል ሴቶች፣ ሕጻናት እና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኀላፊ ብርቱካን ሲሳይ የልማት ኀብረቶች የጋራ ዓላማ እና ግብ ያላቸው እና በአንድ ቀበሌ ውስጥ በተቀራረበ መልክዓ ምድራዊ የጉርብትና ምኅዳር ውስጥ የሚገኙ ሴቶች በየዘርፉ ሊኖራቸው የሚገባውን ተሣትፎ እና ተጠቃሚነት በላቀ ደረጃ ለማሳደግ ተደራጅተው የሚንቀሳቀሱበት መኾኑን ገልጸዋል፡፡

ይህን ሥራ የበለጠ በማጠናከር በልማት ሞዴል የኾኑ ሴቶችን ቁጥር ለማብዛት የአደረጃጀት ለውጦች እንደ ሀገር እየተሠራ እንደኾነም ገልጸዋል።

ሴቶች ላይ መሥራት ለቤተሰብ፣ ለማኅበረሰብ እና ለሀገር መሥራት ነው ያሉት ኀላፊዋ በተለይ ሴቶች በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ተሰማርተው በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲኾኑ የገንዘብ ተቋማት ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት አቅም እንዲኾኑ አስገንዝበዋል።

ሴቶችን በሁሉም ዘርፍ ከተናጠል ይልቅ በተደራጀ አግባብ ማሳተፍ ይገባል ነው ያሉት።

በጤና፣ በትምህርት፣ በግብርና፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና ምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ፣ በቁጠባ ባሕል ኑሮን በማሻሻል፣ ጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶችን እና የኃይል ጥቃቶችን በመከላከል፣ አካባቢን እና የተፈጥሮ ሐብትን በመንከባከብ በሌሎችም ዘርፎች የሴቶችን ተሣትፎ እና ተጠቃሚነት ማጎልበት እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የፖለቲካ እና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኀላፊ ዘሪሁን ፍቅሩ (ዶ.ር) የገጠሙንን ማኅበራዊ ቀውሶች መሻገር የሚቻለው የችግሮችን መነሻ ለይቶ ለመፍትሄ በመሥራት እንደኾነ ገልጸዋል። ሴቶች ላይ የሥነ ልቦና ጫና የፈጠሩ፣ ተጠቃሚነታቸውን የጎዱ ማኅበራዊ ስብራቶች በዚህ ወቅት ተፈጥረዋል ነው ያሉት።

ይህን መቀየር የሚቻለውም በጋራ እና በትብብር ሴቶች ተጠቃሚነት ላይ በመሥራት ነው ብለዋል።

የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይ ባለፉት ጊዜያት የተደራጀ የሕዝብ አቅምን በማሳደግ፣ ሴቶችን በየደረጃው ተሳታፊ እና ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችሉ ተግባራት መሠራታቸውን ተናግረዋል።

የተሻሻለው የሴቶች የልማት ጥምረት አሠራር እና አደረጃጀት ወቅቱን እና ሕዝባችንን የሚመስል እና የሚመጥን ኾኖ እንደ ተደራጀም አቶ ይርጋ ገልጸዋል።

የሴቶች የልማት ኅብረት ጥምረት የልማት፣ የመልካም አሥተዳደር፣ የዴሞክራሲ እና የሰላም አጀንዳዎችን በመፈጸም እና በማሳለጥ ረገድ የሚኖራቸው ጠቀሜታ ወሳኝ መሆኑንም አስገንዝበዋል፡

Amhara Police Commission

11 Jan, 11:37


ከአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ!!!

መንግስት ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ በጠረጴዛ ዙሪያ ተወያይትን እንፍታ በሚል የሰላም በር ከፍቶ በጫካ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በርካታ ኃይሎችን በፍቅር ተቀብሎ ወደ ቀደመ ሰላማዊ ህይወታቸው እየመለሰ ባለበት በዚህ ወቅት ሰላምና የሰላም አውድ የማይመቻቸው የታሪካዊ ጠላቶቻችን ተልዕኮ ተሸካሚ የሆኑ ፅንፈኛ ኃይሎች አሁንም በዜጎች ላይ የጭካኔ በትራቸውን ከማሳረፍ ወደኋላ አላሉም።

የሚከሰቱ ችግሮችን በውይይትና በንግግር የመፍታት ልምምዱ እያደገ የመጣበት ዓለም ላይ እንዳለመታደል ሆኖ በክልላችን ብሎም በብሔ/አስተዳደራችን የሚንቀሳቀሱ ፅንፈኛ ኃይሎች ከዓለማዊ አውድ የራቁ፣ በሀሳብ ሳይሆን በጠመንጃ የሚያምኑ፣ የዜጎችን የአስተሳሰብ የዕድገት ደረጃ በውል ያልተገነዘቡ የሀሳብ ድርቀት የያዛቸው ስለሆኑ የዜጎችን ስቃይ እያራዘሙ ይገኛሉ።

የሰላም ሀሳብ ከውስጡ ማመንጨት ያቆመው ይህ ፅንፈኛ ኃይል ግብሩም፣ ተግባሩም ከሰላም አማራጭ ይልቅ ህዝብ መግደል፣ መዝረፍ እና ማፈናቀል የዕለት ተዕለት ተግባሩ ካደረገ ሰነባብቷል። ይህም ፅንፈኛ ኃይል አሁን ላይ ደግሞ ተስፋ እየቆረጠና ዕድሜው እያጠረ መሆኑን ተረድቶ የለመደውንና ያደገበትን አረመኔያዊ አውሬያዊ ድርጊቱን መፈፀሙን ቀጥሏል።

በብሄረሰብ አስተዳደራችን በዳንግላ ወረዳ ጊሳ ቀጠና አካባቢ የህዝብና የመንግስት ተልዕኮ ይዘው በማስፈፀም ላይ የነበሩ የወረዳ አስተዳዳሪውን ጨምሮ አብረውት የነበሩ አመራሮችን ይህ ፅንፈኛ ኃይል አፍኖ በመውሰድ በዛሬው ዕለት ጥር 03/2017 ዓ.ም በግፍ ረሽኗቸዋል።

እነዚህ ህይወታቸውን ያጡ አመራሮቻችን የህዝብና የመንግስትን ተልዕኮ ለማስፈፀም ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ ህ/ሰቡን በልማት እና በመልካም አስተዳደር ተጠቃሚ ለማድረግ ቀን ከሌት ሲተጉ የነበሩ ቅንና ታታሪ የህዝብ ልጆች ነበሩ።

ሀዘናችን መሪር ቢሆንም ወንድሞቻችን ለጥይት ግንባራቸውን ሰጥተው የተሰውለትን ዓላማ ከዳር ለማድረስ የብሔ/አስተዳደሩና የወረዳው አመራር ህዝቡን በመያዝ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ አድማ መከላከልና ጥምር ሀይል ጋር በመሆን ከምንጊዜውም በላይ በቁጭት፣ በቅንጅት እና በቁርጠኝነት ፅንፈኛውን የማፅዳት ኦፕሬሽኑን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

የአዊ ብሔ/አስተዳደር ህዝብም ይህንን ነውረኛና ፅንፈኛ ኃይል ከመንግሥት የፀጥታ ሀይል ጎን ሆኖ የማፅዳት ዘመቻውን አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ እናስተላልፋለን።

በመጨረሻም ለሟች ቤተሰቦች፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው፣ ለአዊ ብሔ/አስተዳደር ህዝብ፣ ለክልላችንና ለሀገራችን ህዝብ መፅናናትን ከልብ እንመኛለን። ለተሰውት ነፍስ ይማር

Amhara Police Commission

11 Jan, 10:56


በሙስና ወንጀል የተከሰሱ በስራትና በገንዘብ መቀጮ ተቀጡ ።

በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በጋዝጊብላ ወረዳ የሙስና ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች በፅኑ እስራት ተቀጥተዋል።

1ኛ ተከሳሽ አበበ ጌቴው በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር በጋዝጊብላ ወረዳ የአስ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት ሠራተኛ ሲሆን በፊት የመዘጋጃ ቤቱ ኃላፊዎች በነበሩና ወንጀሉ ሲፈፀም ከተቋሙ በለቀቁ ግለሰቦች ስምና ፊርማ በመጠቀም በከተማው 01 ቀበሌ ላይ ለሁለተኛ ተከሳሽ አበራ ክብረት የ 150 ካ/ሜ ቦታ ሀሰተኛ ሰነድ አዘጋጅቶ በመስጠቱና ድርጊቱን ለመፈፀም ከሁለተኛ ተከሳሽ 38,000.00 ብር ጉቦ መቀበልና በፈፀመው ሀሰተኛ ሰነድ ማዘጋጀት ወንጀል ተከስሷል።
2ኛ ተከሳሽ አበራ ክብረት በጋዝጊብላ ወረዳ አስ ከተማ ከተማ 01ቀበሌ በአንደኛ ተከሳሽ ተዘጋጅቶ የተሰጠውን ሀሰተኛ ካርታና ፕላን ሲገለገል በመገኘቱ በሀሰተኛ ሰነድ መገልገል ወንጀል የተከሰሰ እና ይህንን ተግባር እንዲፈፀም ለአንደኛ ተከሳሽ 38, 000 ብር ጉቦ መስጠት ወንጀል ተከሷል።

የወንጀል ድርጊቱን የጋዝጊብላ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት በማጣራት መዝገቡን ለዋግኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ፍትህ መምሪያ ልኳል። የፍትህ መምሪያው የወንጀል የሥራ ሂደትም መዝገቡን ከመረመረ በኋላ በ1ኛ ተከሳሽ ላይ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/2007፣ አንቀጽ 23 (1) እና አንቀጽ 10 (1) በመተላለፍ፣ 2ኛ ተከሳሽ የአዋጁን አንቀጽ 23 (1) እና አንቀጽ 25 (1) የተመለከተውን በመተላለፋቸው በእያንዳንዳቸው ክሶችን በማዘጋጀት ለብሄረሰብ አስተዳደር ዞኑ ከፍተኛ ፍ/ቤት ክስ አቅርቦ ክርክር ሲደረግ ከቆዬ በኋላ ፍ/ቤቱ ታህሳስ 25 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት 1ኛ ተከሳሽ በሁለቱም ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ 3 ዓመት ጽኑ እስራትና በ 3, 000 ብር መቀጮ እንዲቀጣ፣ 2ኛ ተከሳሽ በሁለቱም ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ 2 ዓመት ጽኑ እስራትና በ 1, 000 ብር መቀጮ እንዲቀጣ ውሳኔ ተሰጥቷል ሲል የብሄረሰብ ዞኑ አስተዳደር ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ያደረሰን መረጃ ያሳያል።

Amhara Police Commission

11 Jan, 10:33


"የሰራዊቱን የጤና ሁኔታ በተሻለ መንገድ ለመከታተል የሚያስችል የባለሙያም የቁሳቁስም አቅም ገንብተናል።"
በአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን የጤና ዋና መምሪያ ኃላፊ
ረዳት ኮሚሽነር ስዩም ተፈራ

የሰራዊቱን የህክምና አገልግሎት በማዘመን የተሻለ ተግባር ለመወጣት የሚያስችል ቁመና ላይ መሆኑን የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ጤና ዋና መምሪያ ኃላፊ ረ/ኮሚሽነር ስዩም ተፈራ ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለው እንደተናገሩት ህክምና ማዕከሉ የኮሚሽኑ ክሊኒክ ወደ ጤና ጣቢያ ያደገ ሲሆን አሁን ላይ ብቁ ባለሙያዎች ያሉትና ተወዳዳሪ የሚባል አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ በመጥቀስ ሰራዊቱ ጤናማ ሆኖ ጤናማ ተግባር ይፈፅም ዘንድ የሚጠበቅበትን ሚና እየተወጣ ይገኛል ነው ያሉት።

ጤናማ ማህበረሰብ ለመገንባት ጤናማ ሰራዊትን መፍጠር ግድ ይላል ያሉት ረዳት ኮሚሽነር ስዩም ከምንም ነገር በላጩ ጤና ነውና የሰራዊቱን ሁለንተናዊ ጤና ለመጠበቅ የምንችለውን ተግባር እየተወጣን ነው ብለዋል።

በቀጣይም የሚጎል የህክምና ቁሳቁሶችን በማሟላት ከዚህ የተሻለና የበለጠ ውጤት የሚያስገኝ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።

Amhara Police Commission

11 Jan, 08:31


ህገወጥ ጥይት በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ አስታወቀ።

በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዝቋላ ወረዳ 012 ቀበሌ ተከማችቶ ለፅንፈኛው ቡድን ሊተላለፍ የነበረ 1129 ህገ ወጥ ጥይት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የዋግኽምራ ዞን ፖሊስ መምሪያ ገለፀ።

በሰላም ወዳዱ የአካባቢው ማህበረሰብ ጥቆማ 135 የብሬን ጥይት እና 994 የክላሽ ጥይት ጠቅላላ ድምር 1129 ጥይቶች መያዙን እና ምርመራው የቀጠለ መሆኑን የዝቋላ ወረዳ ፖሊስ መግለፁን ነው የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ያስታወቀው።

የወረዳው ፖሊስ ፀረ ሙስና ወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ዋና ሳጅን ፈንቴ ካሳው እንደገለፁት ታህሳስ 30/2017 ዓ.ም ሌሊት 6:30 አካባቢ ዝቋላ ወረዳ 012 ቀበሌ አወጣ መኳንንቴ የተባለው ተጠርጣሪ ከላይ የተጠቀሰውን የብሬንና የክላሽ ጥይት ፍሬ ይዞ በመገኘቱ ምርመራ የቀጠለ ሲሆን ቀጣይ የምርመራ ውጤቱ ሲጠናቀቅ ዝርዝር መረጃ እና ውሳኔውን የሚያሳውቁ መሆኑን አክለው አሰታውቀዋል ።

Amhara Police Commission

11 Jan, 07:39


ዘጠኝ ህፃናትን አስገድዶ የደፈረው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ።

በሰሜን ወሎ ዞን በራያ ቆቦ ወረዳ የቆቦ ከተማ ኗሪ የሆነው ወጣት ፈንታው አድሴ የተባለ ግለሰብ እድሜያቸው ከ5 እስከ 9 አመት የሚሆኑ ዘጠኝ ህፃናትን በመድፈር ወንጀል ተከሶ በ25 ዓመት ፅኑ እስራት መቀጣቱን ራያ ቆቦ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ የቆቦ ከተማ አስ/ር ፖሊስ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ክፍል ምርመራውን በሰዉና በህክምና ማስረጃ በማጠናከር መዝገቡን ለራያ ቆቦ ወረዳ ፍትህ ፅ/ቤት ልኳል።

መዝገቡ የደረሰው የወረዳው ፍርድ ቤትም ጥር 1 ቀን 2017 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሹን ያርማል እሱንም ሌሎቹንም ያስተምራል ያለዉን የ25 ዓመት ፅኑ እስራት እና የ10,000 ብር የገንዘብ መቀጮ ወስኖበታል።

በፍርድ ሂደቱ አስተያየታቸዉን የሰጡት የተጎጅ ቤተሰቦችም ዉሳኔዉ ማንኛውም ሰዉ ወንጀል ፈፅሞ በመሰወር ከጥፋት ማምለጥ እንደማይችል የተረጋገጠበትና ከወንጀል ድርጊት መታቀብ እንደሚገባዉ የሚያስተምር ፍርድ ነዉ ሲሉ ተናግረዋል።
ምንጭ፦የራያ ቆቦ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ቢሮ
እናንተስ ምን አስተያየት አላችሁ?

Amhara Police Commission

11 Jan, 07:34


ለምግብነት አገልግሎት ሊውል የተዘጋጀ ባዕድ ነገር በፖሊስ ተይዟል።

በትናንትናው ዕለት ጥር 2/2017 ዓ/ም ባህርዳር ከተማ ቀበሌ 14 አቡነ ሃራ ገበያ የተበላሸ በርበሬ ከበአድ ነገር ጋር የተቀላቀለ ለምግብ አገልግሎት እንዲውል የተደበቀ ወፍጮ ቤት ላይ በመዘጋጀት ላይ የነበረ ከመድሐኒት እና ምግብ ቁጥጥር ባለስልጣን እና ከጤና መምሪያ ጋር በመሆን 906 ኩንታል በርበሬ በህግ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ ይገኛል።

Amhara Police Commission

06 Jan, 12:17


ያለሰምሪት ሲንቀሳቀሱ የተገኙ ባጃጆች እና በተለያዩ የሰርቆት ወንጀል የተጠረጠሩ ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ገለፀ።

አማራ ፖሊስ ታህሳስ 28/2017 ዓ/ም
የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ የሰሞኑን በዓላትን አሰመለክቶ በተሰራ ልዩ ክትትል ከሌላ ከተማች የገቡ በህገ ወጥ መንግድ ያለሰምሪት ሲንቀሳቀሱ የተገኙ ባጃጆች እና በተለያዩ የስርቆት ወንጀሎች የተጠረጠሩ ግለሰቦች እና የተሰረቁ እቃዎችን በመግዛት የተጠርጠሩ ግለሰቦችን በልዩ ኦፕሬሽን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር አበባው አሻግሬ ገለፀዋል።

እንዴ ኮማንደር አበባው ገለፃ በደሴ ከተማ ከሌሎች አካባቢዎች ወደ ከተማዋ በመግባትና በስርቆት የተሰማሩ ያለ ሰሌዳ የሚያሽከረክሩ፣ስምሪት የለላቸው፣ አንፀባራቂ የደንብ ልብስ ሳይለብሱ የሚያሽከረክሩ በድምሩ ከ28 በላይ የሶስት እግር ተሽከርካሪዎችና በተለያዩ የስርቆት ወንጀሎች እና በተለይ የተሰረቁ እቃዎችን በመግዛት የተጠረጠሩ 34 ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ተናግረዋል።

ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተበራከተ የመጣዉን ስርቆት ወንጀል ለመከላከል መምሪያው እቅድ በማውጣት እና የተለያዩ የኦፕሬሽን ስራዎች ሲሰራ መቆዬቱን እና በዚህ ልዩ ኦፕሬሽንም በቁጥር ከ7 በላይ የተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ 3 ቴሌቪዥኖች እና ሌሎች በርካታ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችች መያዛቸውን በመግለፅ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ኮማንደሩ አብራርተዋል።

የከተማውን ማህበረሰብ ሰላም ለማስጠበቅና ከየትኛውም ዘርፊያና ስርቆት ለመከላከል የከተማው ፖሊስ አሁንም በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ተገልፆል።

የከተማው ነዋሪ አሁንም በማንኛውም ጉዳይ አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከተ ጥቆማውን ለከተማው ፖሊስ በመስጠት የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ኮማንደር አበባው ጥሪ አቅርበዋል።

መረጃው፦ደሴ ከተማ አሰተዳደር ፖሊሰ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ነው።

Amhara Police Commission

05 Jan, 07:56


ጥንቃቄ!!

በእርጋታ እናሽከርክር

ባህር ዳር ከተማ ቀበሌ አስራ ስድስት ጉዶ ባህር አካባቢ ጀአር ማደያ ታህሳስ 26/2017 ዓ/ም ከምሽቱ 11፡30 ሰዓት ከመሸንቲ በኩል ወደ ባህርዳር መግቢያ የሰሌዳ ቁጥር 3_28467 አ.ማ የህዝብ ማመላለሻ መስመር በመሳት በተቃራኒ አቅጣጫ ከሚመጣ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3- 81088 ከሆነ ሲኖ ትራክ ገልባጭ ጋር በመጋጨት እስካሁን ባለን መረጃ 6 ሰው የሞተ ሲሆን በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል። የአዳጋው መንስኤ እየተጣራ ሲሆን ፖሊስ ከትራፊክ አደጋ ራሳችንን እንጠብቅ ብሏል።

Amhara Police Commission

03 Jan, 17:20


ድጋፍ ተደርጎላቸዋል

የፖሊስ ተቀዳሚ ተግባር ወንጀልና ወንጀለኛን በመከላከል የማህበረሰቡን ሰላም ማረጋገጥ ነው።ይሁን እንጂ በማህበረሰቡ ውስጥ የሚስተዋሉ ማህበራዊ ችግሮችን በእኔነት ስሜት መፍታት እና ኃላፊነት መውሰድም እንዲሁ ተጓዳኝ ተግባሩ ነው።

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽንም የኮሚሽኑ ስታፍ አባላትና አመራሮች ማህበር በማቋቋም ከደመወዛቸው በሚያዋጡት ገንዘብ ማህበራዊ ችግር ላለባቸው ግለሰቦች እርዳታ ያደርጋል።ማህበሩም ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ ለግለሰቦቹ ወጫቸውን በመሸፈን እና የተለያዩ የበዓል መዋያ ወጮችን በመሸፈን ስራውን ያከናውናል።

በማህበሩ ድጋፍ የሚደረግላቸው አካላት በቁጥር ጥቂት የማይባሉ ሲሆኑ ሁለት ልጆች ራሳቸውን በመቻል ከማህበሩ ወጥተዋል።

ዘንድሮም ለመጭው የገና በዓል መዋያ ይሆን ዘንድ ለእያንዳንዳቸው ድጋፍ በማድረግ እንኳን አደረሳችሁ ተብለዋል።

Amhara Police Commission

02 Jan, 13:35


ታግተው የነበሩ መምህራን ተለቀቁ።

ፅንፈኛው ቡድን አግቷቸው የነበሩ መምህራንን የምስራቅ ዕዝ ክፍለ ጦር አሥለቀቀ።

በባህርዳር ዙሪያ የመሸንቲ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን የነበሩ ቀደም ብሎ በፅንፈኛው ሃይል ታግተው የነበሩ ሲሆን የምስራቅ ዕዝ ክፍለ ጦር የሰራዊት አባላት ሥልታዊ ጥበብን ተጠቅመው ማሥለቀቅ ችሏል ።

የክፍለ ጦሩ አዛዥ ኮሎኔል ግፋወሰን አበበ ፅንፈኛው ሃይል የክልሉን ወጣቶች የወደፊት እጣ ፈንታ በማጨለም ክልሉ ወደ ባሰ ቀውስ እንዲገባ 14 መምህራኖችን አግቶ መቆየቱን ጠቁመው ሰራዊቱ ባደረገው የተጠናከረ ስምሪት ማስለቀቅ ተችሏል ብለዋል።

አሁን የተገኘውን አንፃራዊ ሰላም የበለጠ ለማጠናከር በአካባቢው በተለየዩ ቦታዎች በርካታ ስምራቶችንና ድንተኛ አሰሳዎችን በማድረግ ጭፍን አመለካከት ያለውን ቡድን ማሽመድመድ ችለናል ሲሉ ተናግረዋል።

ዘረፊው ቡድን ተማሪዎች በትምህርት ገበታቸው ላይ እንዳይገኙ የሚያደርገው የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ አልበቃው ብሎ በትምህርት ቤቶች ላይ የጥፋት ሴራውን እያራመደ መሆኑን ገልፀዋል።

በአካባቢው የሚገኙ መሠረተ-ልማቶች፣ ትምህርት ቤቶችና የመንግስት ተቋማት ለማህበረሰቡ ግልጋሎት እንዲሰጡ የአካባቢው ማህበረሰብ፣ ወጣቱና የፀጥታ ሃይሉ ከሰራዊቱ ጎን በመሆን የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ አሳስበዋል።

ምንጭ፦የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት

Amhara Police Commission

02 Jan, 13:15


የቤን እንሰሳቶችን በዘረፈው ፅንፈኛ ሀይል ላይ እርምጃ መወሰዱ ተገለፀ።

በመንዝ ጌራ ምድር ወረዳ አመድ ዋሻ ቀበሌ ትላንት ሌሊት መነሻውን ከግሼ ራቤል በማድረግ ያላረባውን በመንዳት ፣ያልዘራውን በማጨድ የሚታወቀው ፅንፈኛ ሃይል ከሰላም አስከባሪዎች ቤት በመግባት የከብት እና የፍየል እንዲሁም የበግ ዝርፊያ ፈጽሞ ወደ ገንዚያ ቆላ ወስዷል።

ይህም አልበቃ ያለው ጽንፈኛው ቡድን ህብረተሰቡን እህል ውሃ እንዲያዋጡ ተልእኮ ሰጥቶ ድሃን እያስቸገረ እንደነበረም ታውቋል።

ይህንን ጥቆማ የሰማው የወረዳው ሰላም አስከባሪ ሀይል በወረዳው ውስጥ ካለው መከላከያ ስራዊት ጋር በመሆን ወደ ቦታው ተንቀሳቅሶ ደቡብ ወሎና ግሼ ራቤል አዋሳኝ ቀጭኔ ጅረት ድረስ በመሄድ ቡድኑ የዘረፋቸውን ንብረቶች ሙሉ በሙሉ አስመልሷል።።

በዚህ ኦፕሬሽንም በርካታ የቡድኑ አባላት እርምጃ የተወሰደባቸው ሲሆን ቡድኑ የሚገለገልባቸው የተለያዩ ክላሾች ከነ ካዝናቸው፣ቦምቦች፣ሙሉ የወገብ ትጥቅ ተማርካል ሲል የመንዝ ጌራ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።

Amhara Police Commission

02 Jan, 12:46


የ9 ዓመት ታዳጊ ህጻን አስገድዶ በመድፈር በደል የፈጸመው ወጣት በ17 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።
ታህሳስ 24/2017 ዓ.ም (አማራ ፖሊስ)

በወልድያ ከተማ አስተዳደር በታላቁ ራስ ዓሊ ክፍለ ከተማ የ9 ዓመቷን ታዳጊ ህጻን በመድፈር የክብረ ንጽህና በደል የፈጸመው ወጣት በ17 ዓመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት ክሱ ከቀረበበት ከወርኃ ሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ጉዳዩን አጣርቶ ወጣቱ ወንጀሉን ስለመፈጸሙ በሰነድ እና በሰው ማስረጃ በማረጋገጥ ትናንት ታህሳስ 23 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት በወንጀለኛው ላይ የ17 ዓመት ጽኑ እስራት ውሳኔ ሰጥቷል።

የዘጠኝ ዓመቷን ታዳጊ አስገድዶ የደፈረው የ17 ዓመቱ ወጣት በሠራው ወንጀል ምክንያት ለሕይወቱ ቁምነገር የሚይዝባቸውን ተጨማሪ 17 ዓመታት በማረሚያ ቤት ለማሳለፍ የፍርድ ውሳኔውን ያለመከላከል አምኖ ተቀብሏል።

ወልድያ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን

Amhara Police Commission

02 Jan, 10:43


ጥንቃቄ!!

የሃሰተኛ የብር ኖት ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረ ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለ።
ታህሳስ 24/2017 ዓ/ም አማራ ፖሊስ

በሰሜን ጎንደር ዞን ጃን አምራ ወረዳ በምትገኘው ዋሰይ ንኡስ ወረዳ ሃሰተኛ የብር ኖት ይዞ ሲንቀሳቀስ የነበረ አለምነው ፈንታ ፀጋዬ የተባለው ተጠርጣሪ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም ከቀኑ 6:00 ሰዓት ላይ እጅ ከፈንጅ ተይዟል።
መነሻውን ጎንደር ከተማ ያደረገው ይህ ተጠርጣሪ አንድ አይነት ሴሪያል ቁጥር ያለው ባለ 200 መቶ የብር ኖት 30,600 (ሰላሳ ሽህ ስድስት መቶ) ብር በመያዝ ከሱቅ እቃ እየገዛ በነበረበት በህብረተሰቡ ጥቆማ መያዙን የጃን አምራ ወረዳ ፓሊስ ወንጀል መከላከል ክፍል ሃላፊ ረ/ኢ/ር ድንቅነው አባይ ገልጿል።
ወቅቱ የባዓላት ጊዜ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከአጭበርባሪዎችና መሰል ድርጊቶች እራሳቸውን እንድጠብቁና ጥርጣሬ ባጋጠመ ጊዜም ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ መልዕከት ተላልፏል።
መረጃው፦የሰሜን ጎንደር ፖሊስ መምሪያ ህ/ግንኙነት ዋና ክፍል ነው።

Amhara Police Commission

02 Jan, 10:33


የበዓል ወቅት ግብይት እና ጥንቃቄ

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ኀላፊ ረዳት ኮሚሽነር መሠረት ደባልቄ በክልሉ የሐሰተኛ የብር ኖት ዝውውር የወንጀል ተግባር በተደጋጋሚ ተከስቷል ብለዋል።

የጸጥታ ኃይሉ ኅብረተሰቡን ግንዛቤ ከማስጨበጥ ባለፈ የወንጀሉን ፈጻሚዎች ተከታትሎ በቁጥጥር ሥር እያዋለ እንደኾነ ገልጸዋል።

ባለፈው ሩብ ዓመት" ከ200 ሺህ ብር በላይ የሐሰተኛ የብር ኖት ሲዘዋወር ተይዟልም "ነው ያሉት ረዳት ኮሚሽነሯ።

የሐሰተኛ የብር ኖት በክልሉ በሁሉም ቦታዎች እንደሚዘዋር የጠቆሙት ኮሚሽነሯ በተለይ በባሕር ዳር ከተማ፣ አዊ እና በዋግ ኽምራ በከፍተኛ ኹኔታ የሐሰተኛ የብር ኖት ዝውውር ተከስቷል፤ በቁጥጥር ሥርም ውሏል ብለዋል።

አርሶ አደሩ እና የንግዱ ማኅበረሰብ በስፋት ግብይት በሚያደርግበት የበዓላት ወቅት ወንጀል ፈጻሚዎች የሐሰት የብር ኖት አሳትመው በመዘዋወር ለኪሳራ ይዳርጋሉ፤ ሰላማዊውን ገበያም ያውካሉ ብለዋል።

ይህም ከግለሰብ ባለፈ የሀገርን ምጣኔ ሐብት እና ገጽታ ይጎዳል ነው ያሉት።

የወንጀል ፈጻሚዎች በተለይ በበዓል ሰሞን የእርድ እንስሳት ወደ ገበያ መውጣታቸውን ታሳቢ ባደረገ መልኩ ሐሰተኛ የብር ኖት በሥፋት ሊያዘዋውሩ ስለሚችል ኅብረተሰቡ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግም ረዳት ኮሚሽነር መሠረት አሳስበዋል።

Amhara Police Commission

02 Jan, 05:06


በሽጉጥ ልጁን የገደለው አባት በእስራት መቀጣቱን ፖሊስ ገለፀ።

ባህርዳር፦ታህሳስ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ( የአማራ ፖሊስ)

ልጁን የገደለው አባት በእስራት መቀጣቱን በደ/ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ የሐይቅ ከተማ ፖሊስ ሚዲያናኮሙኒኬሽን ክፍል ገለፀ ፡፡

አወል ሰይድ የተባለ ግለሰብ በእስራት ሊቀጣ የቻለው በሐይቅ ከተማ ቀበሌ 05 ልዩ ቦታው አስመራ በር ከሚባለው አካባቢ በግምት ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ሰይድ አወል የተባለ ልጁን ከቤት ውጣልኝ በሚል ጭቅጭቅ በያዘው ሽጉጥ ሁለት ጊዜ በመተኮስ ይገድለዋል፡፡

ፖሊስም ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪን በቁጥጥር ስር ካዋለ በኋላ ምርመራውን በቴክኒክና በታክቲክ ማስረጃ ሲያጣራ ቆይቶ ለደቡብ ወሎ ዞን ፍትህ መምሪያ መዝገቡን ይልካል።

የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም ጉዳዩን ሲመረምር ከቆዬ በኋላ ታህሳስ 04 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹን ያርማል ፣ ሌላውንም ማህበረሰብ ያሥጠነቅቃል በማለት በ 14 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣና ኤግዚቢቱም ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ወስኗል ፡፡

ምንጭ ፡- የሐይቅ ከተማ ፖሊስ ሚዲያ ኮሙኒኬሽን ክፍል።

Amhara Police Commission

02 Jan, 04:43


የገና እና የጥምቀት በአል በሰላም እንዲከበር በቂ ዝግጅቶ ማድረጉን የባህርዳር ከተማ ፓሊስ መምሪያ አስታወቀ።

በመምሪያው የወንጀል መከላከል ዋና ክፍል ሀላፊ የሆኑት ኮማንደር ይኸነው ገነት ለዝግጅት ክፍላችን እንደገለጹት በጥር ወር የሚከበሩ በአላቶች ያለምነም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቁ ሰፊ የሆነ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል ብለዋል።
ሀላፊው አክለውም ማህበረሰቡ ለጸጥታ ሀይሉ ያለው አጋዥነት አሁን ላይ ላለው አስተማማኝ ሰላም ጉልህ ድርሻ እንደነበረው ገልጸው ወደፊትም ከጸጥታ ሀይሉ ጎን በመሰለፍ ለከተማችን ሰላም በቁርጠኝነት መስራት ከሁሉም ማህበረሰብ ስለሚጠበቅ ህዝቡ የዘወትር ትብብሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል መልዕክት አስተላልፈዋል።

Amhara Police Commission

01 Jan, 14:20


ህገ ወጥ ጥይት በቁጥጥር ስር ዋለ

በደቡብ ወሎ ዞን ታህሳስ 22 ቀን 2017 ዓም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ሲሆን ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ ደሴ ከተማ ላይ 2,060 /ሁለት ሽህ ስልሳ / የክላሽ ጥይት ከሁለት ተጠርጣሪዎች ጋር በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራው በማጣራት ላይ ይገኛል።
ምንጭ ፡- የደ/ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ ኮሙኒኬሽንና ሚዲያ ዋና ክፍል ነው።

Amhara Police Commission

01 Jan, 11:53


የውንብድና ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

በዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር በሰቆጣ ከተማ ታህሳስ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በጦር መሳሪያ በመታገዝ የውንብድና ወንጀል የፈፀሙ 5 ተጠርጣሪዎች በጠንካራ ክትትል በቁጥጥር ስር ውለዋል።
ተጠርጣሪዎች ሊያዙ የቻሉት ታህሳስ 17 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6:00 ስዓት ሰቆጣ ከተማ አስተዳደር 02 ቀበሌ ቀጠና 3 (ሶስት) የውንብድና ወንጀል ፈፅመው ተሰውረዋል።
ፖሊስ ሰፊ ክትትል በማድረግ ባደረገው የተቀናጀ ስምሪት ተለያዩ አካባቢዎች ተሰውረው የነበሩ የተጠረጠሩ 5 ግለሰቦችን ከነ ጦር መሳሪያቸው በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ ይገኛል።

Amhara Police Commission

01 Jan, 11:21


"የክልላችን ህዝብ የገጠመው የፀጥታ ችግር ለዘመናት የዘለቀ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተፈጠረው የእርስ በርስ ግጭት የመንቀሳቀስ ነፃነትን የገታ ነው ።"የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን

በየዘመናቱ የሚፈጠሩ የፀጥታ ችግሮች በክልላችን ነዋሪዎች ላይ ዘርፈ-ብዙ ጫናዎችን ያስከተሉ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይም በክልሉ በታጣቂ ቡድን አማካኝነት በተፈጠረ ግጭት ምክንያት በነፃነት ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስ እንዳይቻል ያደረገበት ሁኔታ ተፈጥሯል ሲሉ የአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን ተናገሩ።
ኮሚሽነሩ አክለውም በፀጥታ ኃይሉ መስዕዋትነት በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች አሁናዊ የፀጥታ ሁኔታ መሻሻል የታየበት ቢሆንም አሁንም ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊሰሩ የሚገቡ በርካታ ተግባራት ይቀራሉ፤እነዚህን ትኩረት የሚሹ ተግባራትም ከማንኛውም ውዥንብር እና የተሳሳተ ትርክት በመውጣት መፈፀም የፀጥታ አካላቱ ተቀዳሚ ተግባር ሊሆን ይገባል ብለዋል።

የምንሰራቸው ስራዎች ለህዝባችን ሰላምና ደህንነት ሲባል ነው በሚል መንፈስ ስለሆነ በተሰማራንበት ተግባር ሁሉ ህብረተሰባችንን ሊጠቅምና አሁን ከገጠመው የፀጥታ ችግር መውጣት ይቻል ዘንድ ህዝባዊ አገልጋይነታችንን አጠንክረን መስራት ለነገ የማይባል ስራችን ሊሆን ይገባል ሲሉም ነው ኮሚሽነር ደስዬ አሳስበዋል።

Amhara Police Commission

31 Dec, 16:30


❝ተግባር ላይ የዋለው የባር-ኮድ አገልግሎት ለትራፊክ ቁጥጥር እና ለወንጀል መከላከል ስራው  ትልቅ አስተዋፅኦ አበርክቷል።❞ም/ኮ/ር አብርሃም ልየው(በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ማረጋገጫ ዋና ክፍል ኃላፊ)

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ወንጀልንና ወንጀለኛን እንዲሁም የትራፊክ ቁጥጥር ስራን በአግባቡ ለመቆጣጠር የሚያስችል የባጃጅ መለያ ኮድ(ባር ኮድ) አገልግሎት መሰጠቱን መዘገባችን ይታወሳል።


ወደተግባር የገባው አገልግሎቱም ምን ፋይዳ ይኖረዋል?ምንስ ውጤት አመጣ ስንል በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ማረጋገጫ ዋና ክፍል ኃላፊ የሆኑትን ምክትል ኮማንደር አብርሃም ልየውን ጠይቀናቸዋል።

ኃላፊውም እንደገለፁት በከተማዋ የባጃጅ ተሽከርካሪዎች ቁጥር ከፍተኛ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ የሚፈፀሙ ልዩ ልዩ ወንጀሎችን ለማስቀረት ታስቦ የተከናወነ ተግባር መሆኑን በመግለፅ ይህ አሰራር ከተጀመረ ወዲህም ወንጀለኛን በቀላሉ ማንነቱን በማጣራት በቁጥጥር ስር ለማዋል ያስቻለ እንዲሁም በትራፊክ ቁጥጥር ስራ ላይም አዎንታዊ አበርክቶ የታየበት ነው ብለዋል።

አሁን ላይ በከተማዋ ያሉ የባጃጅ አሽከርካሪዎች ባር ኮዱን በመለጠፍ ረገድ የተሻለ እንቅስቃሴ ቢኖርም አንዳንድ ያልለጠፋ ባለባጃጆች ላይም እርምጃ መውሰድ መጀመራቸውን ነው አብርሃም ልየው(ም/ኮ/ር)የገለፁት።

ኃላፊው አክለውም ማህበረሰቡ ባር-ኮድ ያልለጠፉ የባጃጅ ትራንስፖርት ባለመጠቀም እና የሚሳፈሩበትን ባጃጅ ሰሌዳ ቁጥር መዝግቦ በመያዝ እንድሁም ባር_ኮድ የለጠፉ ባጃጆችንም በእጅ ስልክ ስካን በማድረግ ህጋዊነታቸውን በማረጋገጥ ራሱን ከወንጀለኞች መጠበቅ ይኖርበታል በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

Amhara Police Commission

31 Dec, 16:23


ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የHIV/AIDS አገልግሎት ለሁሉም

በአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን የኮሚሽኑ ስታፍ የፖሊስ አመራርና አባላት እንድሁም ሲቪል ሰራተኞች በHIV/AIDS መከላከል እና መቆጣጠር ዙሪያ ዓመታዊ የውይይት መድረክ ተካሄደ።

ዘንድሮም የዓለም ኤድስ ቀን በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለ37ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ36ኛ ጊዜ "ሰብዓዊ መብትን ያከበረ የHIV/AIDS አገልግሎት ለሁሉም"በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።

በአሁኑ ወቅትም እየተዘነጋ ከመጣው የHIV/AIDS በሽታ ራስንም ሆነ ሌላውን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር የሚያስችል የውይይት መድረክ ተደርጓል።

በውይይት መድረኩም ጤናማ ማህበረሰብን ለመገንባት ጤናማ የሆነ የሰላም አስጠባቂና ወንጀል ተከላካይ ሀይል መገንባት ላይ ማተኮር ግድ ስለሚል ሰራዊቱ ጤናውን በመጠበቅ ረገድ ትልቅ ኃላፊነት እንደሚጠበቅበት ተመላክቷል።

Amhara Police Commission

31 Dec, 11:10


አሁን እየታየ ያለውን አንፃራዊ ሰላም በሁሉም አካባቢ በዘላቂነት ለማስፈን የሀይማኖት አባቶች ስለ ሰላም ሊሰብኩና ሊያስተምሩ እንደሚገባ የምዕራብ ጎጃም ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ እድሜአለም አንተነህ ገለፁ።

በዞኑ ከተለያዩ አጥቢያ ቤተክርስቲያናት የተገኙ የሀይማኖት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት በሰላም ማስፈን ዘሪያ በፍኖተ ሰላም ከተማ ውይይት ተካሂዷል።

የምዕራብጎጃም ዞን ዋናአስተዳዳሪ አቶ እድሜአለም አንተነህ የሀይማኖት አባቶች ሀገር ሰላም እንድትሆን ህዝብ በሰላም ወጥቶ እንዲገባና ሰርቶእንዲበላ በሀይማኖታዊ አስተምሮአቸው ሰላምን ሊሰብኩና ሊያስተምሩ ይገባል ብለዋል።

ሰላም ከሌለ የተጀመሩ ልማቶች ይቆማሉ ህዝብ ለእልቂት ይጋለጣል ፣ረሀብ፣በሽታ ይስፋፋል ፣ሀገር ይበተናል፣የሰላም መጥፋት ውጤቱ ይሄ ስለሆነ የሀይማኖት አባቶች ይሄን ሁሉ ችግር በማስወገድ በዞኑ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ወደጫካ የወጡ አካላትን መክረውና ገስፀው ወደ ሰላም ሊያመጧቸው ይገባል ብለዋል።

የፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ማማሩ ሽመልሰ በፀጥታ ችግሩ እየጠፋ ያለውን የሰው ህይወትና የንብረት ውድመት ለመከላከል የሀይማኖት አባቶች የእምነቱ ተከታይ ልጆቻቸውን በየቤተ ዕምነታቸው ሰላም እንዲሰፍን መምከርና ማስተማር ይኖርባቸዋል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊ የሀይማኖት አባቶች እንዳሉት ሰላም ለሁሉም ነገር መሰረት በመሆኑ በየቤተ ዕምነታቸው ከሀይማኖታዊ አስተምሮአቸው መካከል አንዱ ሰላም እንዲሰፍን መምከርና ማስተማር በመሆኑ አሁን ያለው አንፃራዊ ሰላም ዘላቂነት እንዲኖረው ወደ ጫካ የወጡ አካላት በሰላም እንዲመለሱና ሰላም እንዲሰፍን ሀይማኖታዊ ተልእኳቸውን እንደሚወጡ ተናግረዋል።

በየደረጃው ያለን የሀይማኖት አባቶች ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ወደ ጫካ የወጡ አካላትን ካሉበት ቦታ ድረስ በመሄደ በመምከርና በማስተማር ወደ ሰላም አንዲመለሱ በቁርጠኝነት ያለፍርሀት አባታዊ ኃላፊነታችንን እንወጣለን ብለዋል።

Amhara Police Commission

31 Dec, 11:00


በርካታ አደንዛዥ እፅ በቁጥጥር ስር ዋለ

ስምንት ኩንታል አደንዛዥ እፅ በግለሰብ ቤት ተከዝኖ መገኘቱ የገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ ።

አማራ ፖሊስ ታህሳስ 22/2017 ዓ.ም

የገንዳውኃ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽ/ቤት ተወካይ ሃላፊ ኢ/ር ሃይሌ ብርሃኑ አንደተናገሩት ስምንት ኩንታል የሆነ አደንዛዥ እፅ በግለሰብ ቤት ተከዝኖ መገኘቱን ተናግረዋል ።

ሃላፊው አክለው እንደተናገሩ እፁ በከተማ አስተዳደሩ በተለምዶ አቡየ ሰፈር እየተባለ ከሚጠራው አካባቢ መገኘቱን ነው ያስረዱት ።
ግለሰቡ አምርቶ በድብቅ ለመሸጥ ጥረት ሲያደርግ በማህበረሰቡ ጥቆማ መያዙን ተናግረው ሃላፊው አንዳንድ ግለሰቦች አደገኛ እና አደንዛዥ እፅ ከማምረት መቆጠብ እንደሚገባቸው ነው ያሳሳሰቡት ።

እፁ ከማህበረሰቡ በደረሰ ጥቆማ መያዙን የተናገሩት ጽ/ቤት ተወካይ ሃላፊው ፤ ማህበረሰቡ ህገ ወጥ ተግባርን መከላከል ላይ ከፍተኛ ድርሻውን እየተወጣ በመሆኑ ምስጋናቸውን አቅርበው ማህበረሰቡ መሰል ህገወጥ ተግባራትን ሲያጋጥመው መሰል ጥቆማ መስጠትን አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

Amhara Police Commission

29 Dec, 08:00


በግብይት ወቅት ከሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ይጠንቀቁ!!!

ታህሳስ 19 ቀን 2017 ዓ.ም በዋግኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በዝቋላ ወረዳ ፅፅቃ ከተማ በሀሰተኛ ገንዘብ ኖት ግብይት ሲከውኑ የተገኙ ተጠርጣሪዎችን የፓትሮል ቅኝት የሚያደርጉ የፖሊስ አባሎች ተጠርጣሪዎችን ከነ 4,300.00 ሀሰተኛ ብር እጅ ተፍንጅ በቁጥጥር ስር አውለዋል።
ወቅቱ የበዓል ጊዜ በመሆኑ ህብረተሰቡ በማንኛውንም ግብይት ከአጭበርባሪዎች እንዲጠበቁ ጥርጣሬ ባጋጠመ ጊዜም በአቅራቢያው ለሚገኘው ለማንኛውም የፀጥታ አካል ጥቆማ እንድትሰጡ በአክብሮት እንጠይቃለን።

Amhara Police Commission

27 Dec, 12:44


የሀይቅ ከተማ አስ/ር ፖሊስ ፅ/ቤት በህገ ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ የሽጉጥ ጥይት መያዙን ገለፀ ።
           
አህመድን  አብዱል ቃድር  አህመድ የተባለ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ትክል ድንጋይ ወረዳ 03 ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ከጎንደር ታህሳስ 17 /2017 ዓ.ም በመነሳት ወደ ደሴ ከተማ  በኮድ 3 አማ  የሰሌዳ ቁጥር 17031 በሆነ  አባዱላ መኪና እየመጣ ከዞን እና ከብሄራዊ ደህንነት በተሰጠ ጥቆማ  ሀይቅ ከተማ ኬላ ቀበሌ 5 ከረፋዱ  5:00 ሰዓት  ከላይ የተጠቀሰውን ተጠርጣሪ ከነ አሽከርካሪው  ሀይቅ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ እንድገባ ከተደረገ በኋላ አቶ አህመድን አብዱል ቃድር ማር በባሊ ጭኖ ባሊው ሲፈተሽ በባሊው ላይ የምግብ ሳህን በመደረብ ከውስጥ በፊስታል ተቋጥሮ የቱርክ ሽጉጥ ጥይት 1498 የተገኘበት ሲሆን የአባዱላ አሽከርካሪው  ተስፋ ጊወርጊስ ተፈራ ጭምር በድምሩ 2 ሰወችን በቁጥጥር ስር በመዋል ምርመራ እያጣራ መሆኑን የሀይቅ ከተማ ፖሊስ ፅ/ቤት አስታውቋል ።

Amhara Police Commission

26 Dec, 12:37


በዳንግላ ወረዳ ጊሳና እና አካባቢው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የፅንፈኛው ቡድን አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው ለመንግሥት እጅ ሰጡ።

በዳንግላ ወረዳ ጊሳና እና አካባቢው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ በመንግስቱ ገነቴ የሚመራው የፅንፈኛው ቡድን አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው እጅ የሰጡ ሲሆን በዕለቱ ተገኝተው አቀባበል ያደረጉላቸው የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለው ወደ ሠላም ከመጡ ፅንፈኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ የተሰጣችሁን የሰላም ምህረት በመጠቀም የበደላችሁትን ህዝብ ለመካስና ከመንግሥት ጎን ለመሆን እንዲሁም የሚሰጣቸውን ተልዕኮ ለመወጣት ቁርጠኛ ሆናቹ በመምጣታቹ በብሔረሰብ አስተዳደሩ ስም ላቀ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
በተሳሳተ ትርክት መገዳደል ይብቃ ወደ አንድነታችን እንመለስ የሚለውን የሰላም አማራጭ በመጠቀማችሁ ሀገራችን በሰላም እንድታተርፍ አድርጋችኋል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው ሌሎች በጫካ ውስጥ ያሉ የቡድኑ አባላት ከጫካ ወደ ሠላም ተመልሰው ለሰላም ዘብ እንዲቆሙ ማድረግ ይጠበቅባችኋል ነው ያሉት።
የፅንፈኛው አባላትም 02 ብሬን፣ 01ስናይፐር፣ 06 መገናኛ ሬዲዮ፣ 07 የእጅ ቦንብ፣ 20 ክላሽ፣ 35 ኋላ ቀር መሳሪያ፣ 12 የወገብ ትጥቅ፣ O4 የጭስ ቦምብ፣ 989 የክላሽጥይትና 593 የብሬን ጥይት ይዘዉ ለመንግሥት እጅ ሰጥተዋል።
በአቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ የዞኑ ኮር አመራሮች፣ የሚኒ ካቢኒ አባላት፣ የሀይማኖት አባቶችና የወረዳና የከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል።
መረጃው፦ አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ፓሊስ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ነው።

Amhara Police Commission

21 Dec, 10:18


ማስታወቂያ!!! ለአድማ መከላከል ፖሊስ
================
የአማራ ክልል ፖሊስ በበጀት ዓመቱ ተቋሙን በሰዉ ኃይል አቅም ለማጠናከር አቅዶ እየሰራ ይገኛል ። የሰለጠነ የሰዉ ኃይል የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነዉ። ስለሆነም ከተያዘዉ የሰዉ ኃብት ልማት እቅድ አዲስ የፖሊስ አባላትን ማሰልጠን በመሆኑ በርካታ ወጣቶችን በመመልመል ወደ ተቋሙ መቀላቀል ይፈልጋል ።
በመሆኑም ወጣቶች የተከፈተዉን የስራ ዕድል በመጠቀም ህዝብን የማገልገል ክብር መገለጫ ወደሆነው የፖሊስነት ሙያ መስፈርቱን የምታሟሉ በየአቅራቢያችሁ በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን የተቀመጡ መስፈርቶች በተመለከተ፦
በክልሉ ፖሊስ መተዳደሪያ ደንብ ቁጥር 175/2010 የተቀመጡ የምልመላ መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆኖ፦
----------------------------
የምልመላ መስፈርት/መመዘኛ
----------------------------
1. ዜግነቱ ኢትዮጲያዊ የሆነ/ች
2. ለፌዴራሉና ለክልሉ ሕገ-መንግስንቱና ሕገ-መንግስቱን መሰረት አድርገው ለወጡ ሕጎች ተገዥና ታማኝ የሆነ/ች፣
3. ቢያንስ 6ኛ ክፍልና ከዚያ በላይ ያጠናቀቀ/ች
4. ከማናቸውም ደባል ሱሶች የፀዳ/ች፣ መልካም ስነ ምግባር ያለው/ት
5. ከሚኖርበት ቀበሌ አስተዳደር የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
6. ለፖሊስነት የሚያበቃ ሙሉ ጤናማ መሆኑ/ኗ በህክምና የተረጋገጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል ወይም የምትችል፣
7.ዕድሜው/ዋ ከ18 እስከ 28 ዓመት፣
8. ከማንኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆነ/ች፣
9. ቁመት ለወንድ 1.65 ሜትር በላይ የሆነ፣ ለሴት 1.60 ሜትር በላይ የሆነች፣
10. ክብደት ለወንድ 50-70 ኪ.ግ፤ ለሴት 45-65 ኪ.ግ
11. የ7 ዓመት የሥራ ውል ግዴታ በመግባት ሥልጠናው ሲጠናቀቅ በየትኛውም የክልሉ አካባቢ ተመድቦ/ድባ ለመሥራት ፈቃደኛ የሆነ/ች፣
12. ከአሁን በፊት በወንጀል ተከሶ/ተከሳ ያልተቀጣ/ች ወይም የወንጀል ክስ የሌለበት ወይም የሌለባት፣
13. ከአሁን በፊት በማንኛውም የፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ተቋም ሥልጠና ያልወሰደ/ሰደች፤ አባል ሆኖ/ና የማያወቅ ወይም የማታውቅ እንዲሁም የትኛውም የትጥቅ ትግል ተሳትፎ የሌለው/ላት
14. ያላገባ እና ያልወለደ ወይም ያላገባች እና ያልወለደች፣
15. ደሞዝ 5,283 የቀለብ አበል 2200 ቀድምሩ 7,483 ተቋሙ ነፃ ህክምና ያመቻቻል።
ማሳሰቢያ፦
ማንኛውም ዕጩ ተመልማይ በምዝገባ ወቅት ከላይ ከተገለፁት መመዘኛዎች በተጨማሪ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
1. የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና የማይመለስ 1 ፎቶኮፒ፣
2. ከ2 ዓመት በላይ ነዋርነትን የሚያመለክት የቀበሌ ነዋሪነት መታወቂያ ካርድ ይዞ መቅረብና መመዝገብ ይጠበቅበታል፣
3. መዝገባው በሥራ ቀንና በሥራ ሰዓት በክልሉ በሚገኙ የወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤትና ጣቢያዎች ይሆናል፡፡

Amhara Police Commission

20 Dec, 19:45


ማስታወቂያ!!!
================
የአማራ ክልል ፖሊስ በበጀት ዓመቱ ተቋሙን በሰዉ ኃይል አቅም ለማጠናከር አቅዶ እየሰራ ይገኛል። የሰለጠነ የሰዉ ኃይል የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነዉ። ስለሆነም ከተያዘዉ የሰዉ ኃብት ልማት እቅድ አዲስ የፖሊስ አባላትን ማሰልጠን በመሆኑ በርካታ ወጣቶችን በመመልመል ወደ ተቋሙ መቀላቀል ይፈልጋል ።
በመሆኑም ወጣቶች የተከፈተዉን የስራ ዕድል በመጠቀም ህዝብን የማገልገል ክብር መገለጫ ወደሆነው የፖሊስነት ሙያ መስፈርቱን የምታሟሉ በየአቅራቢያችሁ በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን የተቀመጡ መስፈርቶች በተመለከተ:-
በክልሉ ፖሊስ መተዳደሪያ ደንብ ቁጥር 175/2010 የተጠበቁ የምልመላ መስፈርቶች እንደተጠበቁ ሆኖ፦
----------------------------
የምልመላ መስፈርት/መመዘኛ
----------------------------
1. ዜግነቱ ኢትዮጲያዊ የሆነ/ች
2. ለፌዴራሉና ለክልሉ ሕገ-መንግስንቱና ሕገ-መንግስቱን መሰረት አድርገው ለወጡ ሕጎች ተገዥና ታማኝ የሆነ/ች፣
3. ቢያንስ 10/12ኛ ያጠናቀቀ/ች፤ ያላገባ/ች፣ያልወለደ/ች
4. ከማናቸውም ደባል ሱሶች የፀዳ/ች፣ መልካም ስነ ምግባር ያለው/ት
5. ከሚኖርበት ቀበሌ አስተዳደር የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/የምትችል፣
6. ለፖሊስነት የሚያበቃ ሙሉ ጤናማ መሆኑ/ኗ በህክምና የተረጋገጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል ወይም የምትችል፣
7.ዕድሜው/ዋ ከ18 እስከ 25 ዓመት፣
8. የማነኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆነ/ች፣
9. ቁመት ለወንድ 1.65 ሜትር በላይ የሆነ፣ ለሴት 1.60 ሜትር በላይ የሆነች፣
10. ክብደት ለወንድ 50-70 ኪ.ግ፤ ለሴት 45-65 ኪ.ግ
11. የ7 ዓመት የሥራ ውል ግዴታ በመግባት ሥልጠናው ሲጠናቀቅ በየትኛውም የክልሉ አካባቢ ተመድቦ/ድባ ለመሥራት ፈቃደኛ የሆነ/ች፣
12. ከአሁን በፊት በወንጀል ተከሶ/ተከሳ ያልተቀጣ/ች ወይም የወንጀል ክስ የሌለበት ወይም የሌለባት፣
13. ከአሁን በፊት በማንኛውም የፖሊስ እና የመከላከያ ሰራዊት ተቋም ሥልጠና ያልወሰደ/ሰደች፤ አባል ሆኖ/ና የማያወቅ ወይም የማታውቅ፤
14. ያላገባ እና ያልወለደ ወይም ያላገባች እና ያልወለደች፣
15. ደሞዝ 5,283 የቀለብ አበል 2200 ቀድምሩ 7,483 ተቋሙ ነፃ ህክምና ያመቻቻል፤
ማሳሰቢያ፦
ማንኛውም ዕጩ ተመልማይ በምዝገባ ወቅት ከላይ ከተገለፁት መመዘኛዎች በተጨማሪ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
1. የትምህርት ማስረጃ ዋናውንና የማይመለስ 1 ፎቶኮፒ፣
2. ከ2 ዓመት በላይ ነዋርነትን የሚያመለክት የቀበሌ ነዋሪነት መታወቂያ ካርድ ይዞ መቅረብና መመዝገብ ይጠበቅበታል፣
3. ምዝገባው በሥራ ቀንና በሥራ ሰዓት በክልሉ በሚገኙ የወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤትና ጣቢያዎች ይሆናል፤

Amhara Police Commission

17 Dec, 17:41


ህፃናትን መርዛ የገደለችው የቤት ሰራተኛ ላይ የተሰጠው ፍርድ ፀንቷል።

ይግባኝ በመጠየቅ ከእድሜ ልክ ጽኑ እስራት የ23 አመት እስራት እንንዲሻሻል የተደረገላት ተከሳሽ በይግባይ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ሆኗል።

ተከሳሽ ስራ ደጀን የተባለችው ግለሰብ በባህርዳር ከተማ ቀበሌ 14 ፍኖተ አካባቢ በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ በምትሰራበት ወቅት የአሰሪዋን ሶስት ህፃናት በመመረዝ እንዲሞቱ በማድረጓ የባህርዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነሀሴ 9/2015 ዓ/ም በአስቻለው ችሎት የእድሜ ልክ ፅኑ እስራት መወሰኑ ይታወቃል።

የልጆቹ አባት አገባሻለሁ ብሎ ስላታለለኝ በንዴት ግለሰቡን ለመበቀል የሶስቱን ልጆች ምግብ መርዥዋለሁ በሚል በወቅቱ ለፍርድ ቤት የእምነት ቃሏን የሰጠችው ተከሳሽ በዚህም ሁለቱ ህፃናት ወዲያውኑ ሲሞቱ አንደኛዋ የዘጠኝ ዓመት ልጅ በሰዎች እርዳታ ለህክምና በቅታ መትረፋን በወቅቱ መዘገባቸን ይታወሳል።

ይሁን እንጅ የህግ ሂደትን ተከትሎ የተከሳሿ ባቀረበችው የፍርድ ይቀነስልኝ ይግባኝ አቤቱታ ሲያከራክር ቆይቶ ስልጣኑ ያለው ፍርድ ቤት እስራቱን ከእድሜ ልክ ወደ 23 ዓመት ፅኑ ቀንሶትም ነበር።

ወንጀሉ ምንም በማያውቁ ህፃናት ላይ ጭካኔ በተሞላበት አረመኔያዊ ተግባር በእቅድ በሙሉ ሀሳብና ድርጊት የተፈፀመ በመሆኑ የስር ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ መቀነስ የለበትም በሚል ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ ብሎ ሲከራከሩ መቆዬታቸውን የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ የወንጀል ዓቃቢ ህግ አቶ ደረጀ ቁምላቸው ለዝግጅ ክፍላችን ገልጸዋል።
ከዓቃቢ ህግ የቀረበለትን አቤቱታ በጥልቀት ሲመረምር የቆየው ሰበር ሰሚ ችሎትም ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ/ም ባስቻለው ችሎት 23 ዓመቱን ፍርድ በመሻር በስር ፍርድ ቤት በተከሳሿ ላይ ተወስኖ የነበረው የእድሜ ልክ ጽኑ እስራትን በማፅናት ውሳኔው ተፈጻሚ እንዲሆን የወሰነ መሆኑንን ዓቃቢ ህጉ ተናግረዋል።

Amhara Police Commission

17 Dec, 16:36


የኮምቦልቻ ከተማ ትራፊክ ፖሊስ ከትራንስፖርት ቢሮ ጋር በመተባበር ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የተማሪ ትራፊክ ፖሊሶች ስልጠና ሰጠ።

የኮምቦልቻ ከተማ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ሃላፊ አቶ ዳንኤል ኃይሌ እንዳሉት የትራፊክ አደጋ እያደረሰ ያለውን ጉዳት ለመቀነስ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተሳትፎ እንደተጠበቀ ሆኖ የተማሪዎች ሚና ከፍተኛ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮምቦልቻ ከተማ ፖሊስ የትራፊክ ደህንነት ግንዛቤ ማስጨበጫ ክፍል ሃላፊ ኢንስፔክተር ሙሃመድ አደም ትምህርት እና ስልጠናው ስለ ችግሩ የጋራ መረዳትን በመያዝ ለመፍትኤው በትብብር ለመስራት የሚያግዝ መሆኑን አንስተዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው በወሰዱትን ግንዛቤ አግባብ እንደሚሰሩ አሳስበዋል።

በዋና ሳጅን ሙሃመድ አህመድ

Amhara Police Commission

17 Dec, 16:12


በታጣቂዎች በተፈፀመ ጥቃት ንፁሀን ተገደሉ።

በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ገበያ ውለው ሀገር አማን ነው ብለው ወደ ቤታቸው በሚመለሱ ንፁሀን ሰወች ላይ በታጣቂ ሀይሎች በተፈፀመ ጥቃት የ2 ሰወች ህይወት ሲያልፍ በ11 ሰወች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሷል።

ገበያ ውለው ወደ ቤታቸው እየተመለሱ ባሉ ንፁሀን ሰወች ላይ በመቄት ወረዳ አግሪት 05 ቀበሌ ልዩ ቦታው ላይ በታጣቂዎች ቡድን መሪነት ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በተፈፀመ ጥቃት የታርጋ ቁጥር ኮድ 3 አማ 11758 አነስተኛ የህዝብ ማመላለሻ መኪና ውስጥ በነበሩ ንፁሀን ሰወች ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት ደርሷል።

በጉዳቱም ሴቶች እና ህፃናት የሚገኙ ሲሆን የ2 ሰወች ህይወት ወዲያው ሲያልፍ 11 ሰወች ላይ ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል። የቆሰሉ ሰወችም የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።

Amhara Police Commission

15 Dec, 16:49


የሴት አሰልጣኞችን ሁለንተናዊ አቅማቸውን በማጠናከር ለህግ የበላይነት መረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ኅላፊነት እንዲወጡ ተጠየቀ።
አማራ ፖሊስ ታህሳስ 6/04/2017 ዓ.ም

ለ33ኛ ዙር የመደበኛና የአድማ መከላከል ሴት ምልምል የፖሊስ አባላት ከብርሸለቆ ወታደራዊ ት/ቤት ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዩች ጋር በመተባበር የአቅም ግንባታ ስልጠናው ተሰጥቷል ።

የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ የስነምግባር ምግባር መኮንን ኢንስፔክተር መልሽዉ አቸነፍና የብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ት/ቤት ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ አስተባባሪ ሻምበል ገዛችኝ በቀና እንዳሉት በግጭቶችና ጦርነቶች መፈጠር ብዙም ሚና የማይታይባቸው ሴቶች በሚፈጠሩ ችግሮች ቀዳሚ ተጠቂ እየሆኑ ነው። ለዚህም ተሳትፎና ሚናን በህግ አስከባሪ ተቋማት በማሳደግ ለህግ የበላይነት መረጋገጥ የሚጠበቅባቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባም ለሰልጣኞች አሳስበዋል።

ሴቶች በሁሉም ዘርፍ ብቁ፣ለአላማቸዉ ፅኑና ተወዳዳሪ በመሆን ያላቸዉን እምቅ ሀይል መጠቀም አለባችሁ ያሉት ደግሞ የስልጠናው ተሳታፊዎች ናቸው። ሰልጣኞቹ የሚሰጣቸዉን ወታደራዊ ስልጠና በአግባቡ በመወጣት የሚገጥማቸዉን ተፈጥሯዊውና ማህበራዊ ችግሮች ተቋቁመው የሚያጋጥሙ ችግሮችም በብቃት በመጋፈጥ ተልኳቸውን እንደሚወጡ አረጋግጠዋል።

ዘገባው ፦የአማራ ፖሊስ ኮሌጅ ህ/ግንኘነት ክፍል ነው።

Amhara Police Commission

15 Dec, 08:46


"ወቅቱን የዋጀ የፖሊስ ተቋም እንዲኖር የጋራ ጥረት ይጠይቃል" ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን

የአማራ ፖሊስ በተቋማዊ አገልገሎት አሰጣጡና የለውጥ ሂደቶቹ ዙሪያ በተዘጋጁ ሰነዶች ከአመራሮቹ ጋር መክሯል።

በኮሚሽኑ በልዩ ልዩ የሥራ ክፍሎች ለሚገኙ አመራርና ባለሙያዎች፣ በባህርዳር ከተማና አካባቢው ተመድበው ለሚሰሩ የአድማ መከላከል አመራሮች፣ ለቪአይፒ ተቋም ጥበቃ አመራሮች፣ የሰሜን ጎጃም ፖሊስ መምሪያ አመራሮች በተገኙበት ተቋማዊ የለውጥ ሥራዎቻችን አስመልክቶ እስካሁን በተዘጋጁ አራት ሰነዶች ላይ ውይይት ተካህዷል።

ፖሊስ ዓለም አቀፋዊና ህዝባዊ ተቋም ነው። የሀገራችን በተለይም የአማራ ፖሊስ በዚህ እሳቤ የህብረተሰቡን ፍላጎት ያማከለ ተደራሽ አገልግሎት ለመስጠት ጥረት ቢያደርግም በተደራራቢ ምክንያቶች የታሰበውን ያህል አገልግሎት እየሰጠ አይደለም። አሁን በክልሉ የገጠመው የፀጥታ ችግር ደግሞ የአገልግሎት አሰጣጡን ፈትኖታል። ይህንን ታሳቢ በማድረግ ከአደረጃጀት እስከ የመፈፀም ብቃት ሂደት የተስተዋሉ ችግሮች ዙሪያ ኮሚሽኑ ጥናት አስጠንቷል።
በጥናቱ ግኝቶች መነሻነት የተዘጋጀውን የለውጥ ፍኖተ ካርታ የሪፎርሙን አስፈላጊነት፣ ምቹ ዕድሎች፣ እንዲሁም የሚጋጥሙ ሥጋቶች አስመልክቶ ለውይይቱ በቀረቡ ሰነዶች ላይ ተሣታፊዎች ግልፅ ግንዛቤ እንዲይዙ እና የራሳቸውን ተጨማሪ ሐሳብ አስተያዬቶች በግብዓትነት እንዲሰጡባቸው ተደርጓል።

የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደስዬ ደጀን በውይይቱ ወቅት እንዳሉት ተቋም ለትውልድ ለጋራ አንድነትና ፍትሀዊነት ማረጋገጫ ሆኖ እንዲገነባ እና ወቅቱን የዋጀ የፖሊስ ተቋም እንዲኖር የጋራ ጥረት ይጠይቃል ብለዋል።

የመድረኩ ተሣታፊዎች በበኩላቸው የተጀመረው ውይይት የሪፎርም ሥራውን ካማሳለጥ ባሻገር በተቋም ግንባታ ሊታለፍ የማይገባቸውን ቁልፍ ጉዳዮች የሚያግዝ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበው በተቻለ መጠን የተሰጡ የግብዓት አስተያየቶችን በፍጥነት አካቶ ወደ ተግባር እንዲገባ ጠይቀዋል።

ተቋሙ በምን ጉዳዮች ለውጥ እዲያደርግ ትፈልጋላችሁ?

Amhara Police Commission

15 Dec, 06:09


አሸባሪነት በተግባር፣ማንነት በገሀድ ሲጋለጥ

ፅንፈኛው የአማራን ህዝብ ሰላም በማሳጣት የጀመረውን የሽብር ተግባር በማጠናከር ወደለየለት የህዝብ ጠላትነት በይፋ በመሸጋገር ፀያፍ ተግባራትን መፈፀም ከጀመረ ወራቶችን አስቆጥሯል።

የወገኑን ንብረት ከመዝረፍአልፎ ማውደም ጀምሯል፣እየዘረፈ ወገኑን ለመውጋት ብርታት የሰጠውን የገበሬውን አዝመራ ማቃጠል "የበላበትን ወጭት ሰባሪ"የተባለለት እኩይ ሴራ ነው።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ዙሪያ ቀበሌወች የፅንፈኛው ቡድን በአርሶ አደሩ የተሰበሰበ ሰብል ላይ የእሳት ቃጠሎ አካሄደ።

የፅንፈኛ ቡድኑ በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር መንቆረር ክ/ከተማ የቦ አርጀና ቀበሌ በተሰበሰበ የአርሶ አደር የስንዴ ክምር ላይ ጉዳት አድርሷል።
 
በተስፋ መቁረጥ ላይ የሚገኘው ቡድኑ የንፁህ አርሶ አደሮችን ዘጠኝ (9) የስንዴ ክምርና የተሰበሰበ የከብቶች ቀለብ የሆነ ገለባ ጭምር ታህሳስ 5ቀን 2017 ዓ.ም በክብሪት ጭሮ አውድሞ የሸሸ ሲሆን በስፍራው የመንግስት የፀጥታ መዋቅር ፍጥነው በመድረስ ከዚህ በላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ማድረግ መቻሉን የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

Amhara Police Commission

21 Nov, 15:50


በክልሉ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለመገንባት የፀጥታ ተቋማትን የመፈፀም አቅም ማጎልበት ይገባል።

በክልላችን በአለፉት አንድ አመት ከ4 ወር የነበረውን የሰላም ችግር ለመመለስ በኢፌድሪ መከላከያ ሰራዊት እና ፅኑ አቋም ባላቸው የክልሉ የፖለቲካና የፀጥታ መዋቅራችን ለህዝብ በተከፈለው ውድ መሰዋትነት በሰላም ወዳዱ ህዝባችን ሁለንተናዊ ትብብር አሁን እያየነው ላለው የሰላም፣የፀጥታ መረጋጋትና የልማት ስራዎች ውጤታማነት ጉልህ ድርሻ አላቸው።

በክልላችን በሁሉም አካባቢዎች አንፃራዊ የሰላም መሻሻሎች በመኖራቸው የግብርና ምርቶች፣የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ውጤታማ መሆናቸውን አይተናል።ህብረተሰባችንም ለሰላምና ደህንነት ስራው ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት ከፀጥታና ከአመራሩ ጎን በመሰለፍ በየደረጃው ከፍተኛ ተሳትፎና ባለቤት መሆናቸውን ሲያረጋግጡ ተመልክተናል።ተጠናክሮ መቀጠል አለበት።

የአብክመ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የሚያስተባብራቸው የፀጥታ ተቋማት የክልላችንና የሀገራችን ህዝቦች መብትና ጥቅም ማዕከል በማድረግ አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ ውስጣዊ የፀጥታ ተቋማት የመፈፀም አቅም የአመለካከትና የአስተሳሰብ ግንባታ ስራ ላይ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

በዚህ መሰረት ተቋማት በየራቸው ከተልኮ ውጤታማነት አንፃር በመገምገም በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ተልኳቸውን እየተወጡ ይገኛሉ።ይሁን እጂ አንዳንድ የጽንፈኛ ማህበራዊ ሚዲያዎች በአማራ ክልል ህዝብ ሞት ዳቦ የሚቆርሱ ሀይሎች ዛሬም ሞት እየደገሱ ያለቢሆንም የፀጥታ መዋቅራችን እና ህዝባችን እጅ ለእጅ ተያይዘን በክልሉ ዘላቂና አስተማማኝ ሰላም ለማምጣት እየሰራን መሆኑን ቢሮው በአፅንኦት ይገልፃል።
ህዳር 12/2017 ዓ.ም
ባህርዳር
"ሰላም ለሁሉም፣ሁሉም ለሰላም!!
የአብክመ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ

Amhara Police Commission

20 Nov, 14:06


በፖሊስ ተቋም ለረዥም አገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው በጡረታ ለወጡ አመራሮች የምስጋና መርሐ ግብር ተዘጋጅቶላቸዋል።

በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ስር ከወረዳ እስከ ዞን መምሪያ በተለያዩ አመራርነት ያገለገሉ የፖሊስ መኮንኖች የጦረታ ጊዚያቸውን አጠናቀው በመውጣታቸው የብሔረሰብ አስተዳደሩ ፖሊስ መምሪያ ለነበራቸው አርዓያነትና አገልግሎት የምስጋና ፕሮግራም ተዘጋጅቶላቸዋል።
የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዋና አሰተዳዳሪ አቶ ኃይሉ ግርማይ ብሔረሰብ ዞኑ አሁን ያለው አንፃራዊ ሰላም የተገኘው የፖሊስ ተቋሙ እና የፀጥታ መዋቅሩ በከፈለው መስዋዕትነትና በሰራው መልካም አስተዋፅኦ መሆኑን ገልፀው በጡረታ የተገለሉት መኮንኖችም ለአመታትም ሆነ በአሁኑ ሰዓት ለዞኑ ሁለንተናዊ ሰላም ለነበራቸው አስተዋፅኦ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

የብሔረሰብ አስ/ር ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደጀን ወዳጅ በበኩላቸው ከልጅነት እስከ ዕውቀት ለረጅም ጊዜ በፖሊስ ተቋማችን አገልግለው በክብር በጡረታ የወጡ አመራሮቻችን በነበራቸው ቆይታ ለሰሩት መልካም አርዓያነት የምስጋና ፕሮግራም የተዘጋጀው ከወታደርነት እሰከ ኮማንደርነትና ከተመሪነት እስከ አመራርነት በነበረው ሂደት የሚገጥማቸውን ፈተናዎች አልፈው በክብር ለጡረታ መድረስ ትልቅ መታደል ስለሆነም ከነዚህ አመራሮች ትግስትን ፣ህዝባዊነትን፣ ሚዛናዊነትን መውሰድ ይገባናል ብለዋል።

Amhara Police Commission

20 Nov, 07:26


ቲሊሊ ከተማ አስተዳደር እና ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ በአካባቢው ሰላም ለማስፈን ባለፉት ቀናት ሲያሰለጥናቸው የነበሩ የሠላም አስከባሪዎችን አስመረቁ ።

በአዊ ብሔ/አስተዳደር ቲሊሊ ከተማ አስተዳደር እና ጓጉሳ ሽኩዳድ ወረዳ የፀጥታ ችግር በመከሰቱ ለረጅም ወራት በሠላም እጦት ውስጥ መቆየቱ ይታወቃል ።

ከዚህ ችግር በዘላቂነት ለመውጣት የአካባቢውን የፀጥታ ሀይል ማደራጀት እና ማጠናከር እጅግ አሰፈላጊ በመሆኑ ባለፉት ቀናት በቅንጅት ሲያሰለጥኑ የነበሯቸውን የሠላም አስከባሪ አባላትን በዛሬው ዕለት ያስመረቁ መሆኑን ከቲሊሊ ከተማ አሰተዳደር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል ።

Amhara Police Commission

19 Nov, 14:29


"ሰላማችንን በማጽናት ልማታችንን እናስቀጥላለን" የዱርቤቴ ከተማ ነዋሪዎች

በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞን ዱርቤቴ ከተማ አሥተዳደር የተገነቡ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናቅቀው ተመርቀዋል።

ከምረቃ ሥነ ሥርዓቱ በተጨማሪ አመራሩ፣ ኅብረተሰቡ እና በአካባቢው የሚገኙ የመከላከያ አመራሮች በልማት እና በሰላም ጉዳዮች ላይ ከሕዝብ ጋር ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ የተሳተፉት የከተማዋ ነዋሪዎች በሰላም መስፈን እና በልማት ቀጣይነት ላይ አስተያየት ሰጥተዋል።

የመልካም አሥተዳደር ችግር ሲፈጠር ሕዝብ ለጦርነት ይዳረጋልና ያጋጠመን ችግር እንዲቃለል አመራሩ ጠንክሮ መሥራት ያስፈልጋል ተብሏል።

የመከላከያ ሰራዊት ባልተመቸ ሁኔታ ለሕዝብ ሰላም ሲል መስዋዕትነት እየከፈለ ነው ያሉት ነዋሪዎች ሁላችንም ለሰላም ብንሠራ ይህ ሁሉ ችግር አይደርስብንም ነበር፤ አሁንም ለሰላም ትኩረት እንስጥ ብለዋል።

የሰሜን ጎጃም ዞን ዋና አሥተዳዳሪ አሰፋ ጥላሁን ለተመረቁት እና በአዲስ ግንባታቸው ለተጀመሩ የልማት ሥራዎች መሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረከተው መከላከያ ሰራዊት ነው ብለዋል። ምስጋናም ይገባዋል ነው ያሉት።

የልማት ሥራዎቻችን እንዳይቆሙ እንሠራለን። በዞኑ ለዱርቤቴ - ቁንዝላ - ሻውራ 260 ኪሎ ሜትር የአስፋልት መንገድ፤ ለአዴት - ሰከላ 62 ኪሎ ሜትር መንገድ እና ለባሕር ዳር - ዘጌ መንገድ ሥራዎች በርካታ ቢሊዮን ብር መመደቡን ገልጸዋል። እነዚህ መንገዶች ተጠናቅቀው ለኅብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ሰላም ያስፈልጋል ነው ያሉት።

ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የሰላምን ጠቀሜታ ተረድቶ ለሰላም ጠንክሮ መሥራት ይገባልም ብለዋል።

Amhara Police Commission

19 Nov, 10:28


በጎንደር ከተማ የ9 አመት ህፃን ልጅን አግተው በጎርፍ በማስወሰድ በአሰቃቂ ሁኔታ የገደሉ ተከሳሾች እስራት ተቀጡ።

ነሀሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 5፡30 አካባቢ ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 ቀጠና 03 ሽዋ በር አካባቢ ከአቶ ደርበው ታፈረው ግቢ ዶርም ተከራይተው እያለ ወይዘሮ አበባ ፈለቀ የተባለችው ግለሰብ ህፃን ኪብሮን ደርበውን ከግቢ ነይ ብር ልቀበል አብረን እንሂድ በማለት ወደ ቀሃ ወንዝ አቅጣጫ ይዛት በመሄድ ቀሃ ወንዝ አካባቢ ካለ ዋርካ ዛፍ አካባቢ ስትደርስ ባለቤቷ ለሆነው ሙሉጌታ አታሎ ሲሳይ በመስጠት ትመለሳለች።

ሙሉጌታ አታሎ የተባለው ግለሰብም ህፃኗን እንዳትጮህ አፏን በፎጣ በማፈን በመውሰድ ያዛቸው ውብስራ ከተባለ ተባባሪ ግለሰብ ጋር በመሆን ከምሽቱ 1፡30 ሰአት አካባቢ ዝናብ ሲመጣ ህፃኗን ይዘው ወደ ቃሃ ወንዝ አዲሱ ድልድይ በመሄድ ህፃን ኪብሮን ደርበውን ከሙላት ጎርፍ ወርውረው በመጣል ጎርፍ እንዲወስዳት አድርገዋል።

ግለሰቦቹም ህፃኗ በህይወት እንዳለች በማስመሰል ከቤተሰቦቿ 1000,000(አንድ ሚሊዮን ብር)በመጠየቅ ድርድር ጀመሩ።

ግለሰቦቹም ያዘኑና ስለ ጉዳዩ የማያውቁ በመምሰል ከህፃኗ ቤተሰቦች ጋር በመሆን ከህብረተሰቡ ህፃኗን ማስለቀቂያ ብር ሲለምኑ ውለው 800,000(ስምንት መቶ ሽህ ብር) መሰብሰቡን ካረጋገጡ በኋላ ስልክ በመደወል በ800,000 ብር ከወላጆች ጋር ድርድር ይጀምራሉ።

የሟች አባትም የልጄን ድምፅ ካለሳማችሁን ብሩን አልከፍልም በማለቱ እና ለፖሊስ በሰጠው ጥቆማ ተከሳሾች በቁጥጥር ስር ውለው ህፃን ልጅ በመጥለፍ እና በመግደል ወንጀል ተከሰው የፍርድ ሂደቱ ሲጠበቅ ቆይቷል፡፡

የጎንደር ከተማ ፖሊስም ከአብክመ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀል መርማሪ አካላት ጋር በመቀናጀት አስፈላጊውን ምርመራ በማስረጃ በማስደገፍ ለሚመለከተው የፍትህ አካል መዝገቡን ይልካል።

በመሆኑም መዝገቡ የደረሰው የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህዳር 10 ቀን 2017 ለህብረተሰቡዓ.ም በዋለው ችሎት ወ/ሮ አበባ ዘለቀ አያሌውን የ21 ዓመት ፅኑ እስራት ሲወስንባት ዳጊ ደሳለኝ ሲሳይእና ያዛቸው ውብስራ ሃይሌ የተባሉ ወንጀለኞችን የእድሜ ልክ እስራት ቅጣት እንድቀጡ ወስኖባቸዋል።

Amhara Police Commission

18 Nov, 15:40


በተሽከርካሪ ግጭት በደረሠ የትራፊክ አደጋ የአንድ ሠው ህወት አለፈ

በሰሜን ሸዋ ዞን በሞጃና ወደራ ወረዳ ፈረስ መጋለቢያ ቀበሌ ልዩ ቦታው ቀይ አፈር እየተባለ ከማጠራው ሥፍራ ከጣር ማብር ወደ ሠላድንጋይ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ አይሲዙ ቅጥቅጥና ከሠላድንጋ ወደ ደብረብረሀን ሲጎዝ የነበረ ሲኖ ትራክ መኪና በመጋጨታቸው የህዝብ መጫና ቅጥቅጥ ተጭነው ከነበረውት ተሳፋሪ ውስጥ አንድ ሰው ህይወቱ ሲያልፍ አንድ ሠው ላይ ቀላል ጉዳት ደርሷል።
የወረዳው ፖሊስ ጠቅሶ የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል መረጃውን አድርሶናል።

Amhara Police Commission

18 Nov, 15:38


ለወልቃይት ጠገዴ የፖሊስ አመራሮች የማዕረግ እድገት ተሰጠ።

በአማራ ክልል ወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ፖሊስ መምሪያ በስራ አፋፃፀማቸው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ አመራሮች የማዕረግ እድገት ተሰጥቷል።
ከረዳት ኢንስፔክተር ወደ ም/ኢንስፔክተር ሽግግር ላደረጉ 23 የፖሊስ መኮንኖች ነው የማዕረግ ማልበስ ስነ ስርዓት የተከናወነው።
የዞኑ የፓሊስ መምርያ ኀላፊ ኮማንደር ሙላት ማሞ የማዕረግ ሽግግሩ ለህዝብ አግልግሎት የተከፈለ ዋጋ በመሆኑ ከዚህ በላቀ አገልግሎት በክብር መጠበቅ አለበት ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።
መረጃው የዞኑ ህዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ነው።

Amhara Police Commission

18 Nov, 14:54


በሰላም ለሰላም መስራት ለራስም ለወገንም ከእንቁ የከበረ፣ከጊዜው ጋር አብሮ የሚጓዝ የዘመኑ ገድል ነው።

ህዝባችን ሰላም ይሻል፣በጦርነት የጎበጠ ወገቡን በሰላም ቀና ማድረግ ይፈልጋል፣የተሸከመውን ጨካኝ ቀንበር ከትከሻው ማውረድን ይናፍቃል፣በእምባ እና በሀዘን የከረመ ፊቱን ፈገግ ማድረግን አብዝቶ ይመኛል፣በስደት እየተንከራተቱ እግሮቹን፣በልመና እየተሸማቀቁ እጆቹን ማሳረፍ ይፈልጋል።

በገዳይና ሟች ወንድማማቾች፣በአባራሪና ተባራሪ ቤተሰቦች ወላጆች ማልቀስ ሰልችተዋል።በየጊዜው ሰላሜን መልሱልኝ፣ጦርነቱ ይብቃ፣መሰደዴ፣መፈናቀሌ፣መሞት መቁሰሌ፣ከንቱ መከራየ በቃኝ እያለ ተማፅኗል።

አሁን አሁን ግን ተስፋ ሰጭ ጅምሮች እየተከናወኑ ነው። የህዝባችንን ሰላም መመለስ የሚያስችሉ በሰላማዊ መንገድ የእጅ መስጠት በጎ ተግባራት እየተፈፀሙ ነው።

በዚህ ጊዜ እጅ መስጠት ህይወት ከመስጠት የበለጠ ዋጋ አለው።በርካታ የህይወት መስዕዋትነት ተከፍሏል ነገር ግን የተከፈለው ህይወት ዋጋ ሳይሆን ኪሳራ ነው ያመጣው።ትርፋማው መስዕዋትነት ለራስም ለወገንም ሲባል በሰላማዊ መንገድ ወደ ማህበረሰብ በመቀላቀል የራስን ማህበራዊ ሰናይ ተግባር መፈፀም ነው።

ይህም ተግባር በክልላችን የተለያዩ አካባቢዎች በተለያየ ጊዜ በርካታ ታጣቂዎች በሰላማዊ መንገድ እጅ እየሰጡ ናቸው።በየቀኑ ቀላል የማይባሉ ታጣቂዎች ከገቡበት የጦርነት አዙሪት እየወጡ ህይወታቸውንም ማህበረሰባቸውንም እጅ በመስጠት ጥበብ እየታደጉ ነው።

በጎንደር፣በሸዋ፣በወሎ፣በጎጃም ባሉ በርካታ ወረዳዎች እና አካባቢዎች በየዕለቱ ከነ ሙሉ ትጥቃቸው በሰላማዊ መንገድ እጅ የሚሰጡ አካላትም ለቀሪ አጋሮቻቸው ሳይቀር ስለተያዘው የትጥቅ ትግል አክሳሪነት ምክረ ሀሳባቸውን ሁሉ በመስጠትና የተሀድሶ ስልጠና በመውሰድ የጫካ ስጋትና መከራቸውን አሰናብተው ከማህበረሰባቸው ጋር የተረጋጋ ህይወትን እየመሩ ይገኛሉ።

በእኛ በኩልም የተጀመሩ የሰላም ተግባራት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እየተመኘን ህዝባችን ከገጠመው የጦርነት አባዜ ለመውጣት ብቸኛው መፍትሔው ሰላማዊ መንገድ መሆኑን ልብ ማለት ምርጫ ሳይሆን ግደታ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል እንላለን።

Amhara Police Commission

18 Nov, 08:04


"የተማሪ ወላጆች፣መምህራንና ባለድርሻ አካላት በጸጥታ ችግር ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን ትምህርት በማስቀጠል ትውልድን የመታደግ ኃላፊነት ልትወጡ ይገባል!"

     አቶ ማማሩ ሽመልስ
የፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ከንቲባ

በምዕራብ ጎጃም ዞን ፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ባከል አባጠር ቀበሌ ከጓይ ሚካኤል ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ የሰላም፣ልማትና መልካም አስተዳደር ጉዳዮች "ሰላም ለሁሉም፣ሁሉም ለሰላም በሚል መሪ ሀሳብ" ዉይይት ተካሂዷል።

ህብረተሰቡ ሰላምን ከሚያደፈርሱ ድርጊቶች እንዲቆጠብና ለቀበሌዉና ከተማዋ ሰላም የራሱን ድርሻ እንዲወጣ የከተማዋ ከንቲባ አቶ ማማሩ ሽመልስ ተናግረዋል።

ለሰላማቸው  ቀበሌያቸውን ተደራጅተው እንዲጠብቁና ወደ ተሟላ ልማት እንዲሽጋግሩ ያሳሰቡት ከንቲባው ከሰላም በተጨማሪ ለአንድ ዓመት የተቋረጠውን መማር ማስተማር የማስቀጠል ከባድ ኃላፊነት እንዳለባቸው አሳስበዋል።

የዉይይቱ ተሳታፊዎች እንዳሉት ከአንድ ዓመት በላይ በቆየው የሰላም እጦት ለኢኮኖሚያዊ፣ ለማህበራዊ እንዲሁም ለስነ ልቦናዊ ቀውስ ተዳርገናል፤ ከዚህ በኋላ ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥልን እኛም የድርሻችንን ለመወጣት ከከተማ አስተዳደሩ ጎን እንቆማለን ብለዋል።

በዉይይቱ የዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ ምንይችል፣የፍኖተሰላም ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ማማሩ ሽመልስ፣የባከል አባጠር ቀበሌ ነዋሪዎች፣የፍኖተ ሰላም ከተማ አስተዳደር ሰላምና ደህንነት ኃላፊ አቶ አዱኛ መስፍን እንዲሁም ሌሎች የዞንና ከተማ አስተዳደሩ የፀጥታ አካላት ተገኝተዋል።

ዘገባው የፍኖተ ሠላም ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ነው።

Amhara Police Commission

13 Nov, 13:08


ምዕራብ ጎንደር ዞን በገንደውሃ ከተማ አስተዳደር የሰላም አማራጭን ተጠቅመው ምህረት ከገቡ ጋር ውይይት ተደርጓል።

ህዳር 4/2017 ዓ.ም 200 የሚሆኑ ከአሁን በፊት በተለያየ ወረዳ ከፅንፈኛው ጋር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የሰላም ጥሪውን ተቀብለው ወደ ሰላማዊ መንገድ ከተመለሱት ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን በድርጊታቸው በመፀፀት ቀጣይ ከመንግስት ጎን በመሆን አብረው እንደሚሰሩ አረጋግጠው ውይይቱ ተጠናቋል።
ለሰላም መቼሞ አይረፍድም!!

Amhara Police Commission

13 Nov, 11:16


የሰላም ውይይቱ ፍሬ ማፍራት ጀምሯል።

በአማራ ክልል የተፈጠረውን የፀጥታ ችግር ለመቀልበስ የሚያስችሉ በርካታ ህዝባዊ ውይይቶች ተካሂደዋል፣እየተካሄም ይገኛሉ።እዚህ ውይይቶችም ከግጭት በመውጣት ወደ ሰላም ለመግባት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ሁሉም የፀጥታ አካላት ከማህበረሰቡ ጋር በመሆን የደረጓቸው ናቸ።

በዚህም መንግስት ያቀረበውን የሰላምታ አማራጭ በመጠቀም በርካታ ጣቂዎች እጅ እየሰጡ ነው።በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት በሰላማዊ መንገድ እጅ በመስጠት ማህበረሰቡን መቀላቀል ጀምረዋል።

የሰላም በር ሁልጊዜም ክፍት መሆኑን በመረዳት እና እየተደረገ ያለው የትጥቅ ትግል ኪሳራ እንጂ ጥቅም እንደሌለው ቀመረዳት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ታጣቂዎች በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች እጅ በመስጠት ላይ ይገኛሉ።

ከሰሞኑም በምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ዮሀንስ ፣ገንዳ ውሀ፣አብርሃጅራ፣እና በሰሜን ጎንደር ዞን ደባርቅ ከተማ በጥቅሉ 18 የሚደርሱ ታጣቂዎች ከነትጥቃቸው በሰላማዊ መንገድ እጅ በመስጠትና የተሀድሶ ስልጠና በመውሰድ ወደ ማህበረሰቡ ተቀላቅለው መደበኛ ህይዎታቸውን እየመሩ ይገኛሉ።

ይህ ተግባርም ህዝባችን ካለበት የመከራ ህይዎት የሚታደግ ሰናይ ተግባር በመሆኑ ይህ አይነቱ የሰላማዊ መንገድ ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥል ዘንድ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን ይመኛል።

Amhara Police Commission

13 Nov, 09:38


የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ያሰለጠናቸውን የሰላም አስከባሪ አባላት አስመረቀ።

የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ሚሊሻ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ያሰለጠናቸውን የሰላም አስከባሪ አባላት የከተማ አስተዳደሩና የፀጥታ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት አስመርቋል።

በምረቃ ፕሮግራሙ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ተሾመ ዋለ፣የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ስለሽ ተመስገን ፣ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሃላፊ አቶ መልካሙ ሽባባው ፣በሀገር መከላከያ ሰራዊት የምስራቅ ዕዝ የ32ኛ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮለኔል አለምሰገድ ተስፋየ፣ የአብክመ አድማ መከላከል ሎጅስቲክ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር አያሌው አሊ እና የአድማ መከላከል 4ኛ ሻለቃ አዛዥ ኮማንደር ሽመልስ ሃይሉ ተገኝተዋል።

መረጃው የደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር ኮሙዩኒኬሽን ነው

Amhara Police Commission

13 Nov, 09:29


በዳንሻ እና አካባቢው የፅንፈኛው ቡድን አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው እጅ ሰጡ።

ህዳር 04 ቀን 2017 ዓ.ም

በዳንሻ እና አካባቢው በስምሪት ላይ ለሚገኘው የሰሜን ምዕራብ ዕዝ ኮር ሠራዊት በርካታ የፅንፈኛው ቡድን አባላት ከነሙሉ ትጥቃቸው እጅ እየሠጡ ነው።

ሜጀር ጄኔራል ሰለሞን ቦጋለ ወደ ሠላም ከመጡ ፅንፈኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ሠራዊቱ ተልዕኮውን በአግባብ የሚፈፅም መነሻው መድረሻው የሆነውን የሀገርና ህዝብን ሰላም በመጠበቅ ልማትን የማረጋገጥ ግብ ስላለው ላቆሰለው ለገደለው ምህረት የሚሰጥ ለአንድነት እና ለፍቅር የቆመ የኢትዮጵያ መልክ ነው ብለዋል።

ወዶ ገቦች በተሳሳተ ትርክት መገዳደል ይብቃ ወደ አንድነታችን እንመለስ የሚለውን የሰላም አማራጭ በመጠቀማችሁ ሀገራችን በሰላም እንድታተርፍ አድርጋችኋል ያሉት ጄኔራል መኮንኑ ሌሎች በጫካ ውስጥ ያሉ የቡድኑ አባላት ከጫካ ወደ ሠላም ተመልሰው ለሰላም ዘብ እንዲቆሙ ማድረግ ይጠበቅባችኋል ነው ያሉት።

ኮሩ በተካሄዱ የሰላም ኮንፍረንሶች ህዝቡ በየወረዳው ባቋቋማቸው ሰባት የሰላም ካውንስሎች አማካኝነት በመደናገር የወጡ የቡድኑ አባላት ወደ ቀደመ ሰላማዊ ህይወት እንዲመለሱ የማመቻቸት ስራ እየሰራ እንደሆነም ሜጀር ጄነራል ሰለሞን ቦጋለ አስረድተዋል።

በቀጠናው የሚገኘው ኮር አዛዥ ብርጋዲየር ጄኔራል ወርቅነህ ጉደታ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ለምለም ሀገር ሆና እያለች ማልማት፣ ማበልፀግና ወደ ከፍተዋ ማሻገር ሲገባ ብጥብጥና ሁከት በማስነሳት ወጣቱ ሀገርን የማተራመስ የታሪካዊ ጠላቶቻችን ሴራ ማክሸፍ እንጂ ማስፈፀሚያ መሳሪያ መሆን አይገባም ሲሉ አስገንዝበዋል።

መደመር ለአንድነት የሚል እሳቤን በማስረፅ ሀገራችን አንድ ግን ብዙ ሆና ማየት የትውልዱ ስራ መሆኑን አውቃችሁ መንግስትና ህዝብ የሰጣችሁን እድል በአግባቡ ልትጠቀሙበት ይገባል ብለዋል ።

መረጃው የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ነው።

Amhara Police Commission

12 Nov, 14:21


ወላጅ አባቱን የገደለው ግለሠብ በእስራት ተቀጣ።

ተከሳሽ አብረሀም አሳልፈው አማረ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የኢ.ፊ.ዲ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 539/1/ሀ/ በመተላለፍ ሠውን ለመግደል በማሠብ ጥር 18/ 2016 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 3:00 ሠዐት በሚሆንበት ጊዜ ሰሜን ሸዋ ዞን ሸዋሮቢት ከተማ 01 ቀበሌ ልዩ ቦታው ጮረቃ ሠፈር እየተባለ ከሚጠራው ሥፍራ ሟች ወላጅ አባቱን አሳልፈው አማረ የተባለውን ግለሠብ ከመኖሪያ ቤታቸው አልጋ ላይ በተኛበት በያዘው መጥረቢያ አንገቱን በመምታት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርጎታል።
ከፖሊስ የቀረበውን የምርመራ መዝገብ የተመለከተው የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በፈፀመው የሠው መግደል ወንጀል በሠው ማሥረጃና በሠጠው የእምነት ቃል በመረጋገጡ በጥቅምት 29/2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽን ያስተምረዋል ሌሎችንም ያስጠነቅቃል በማለት ፍ/ቤቱ በተከሳሽ አብርሃም አሳልፈው ላይ የ13 ዓመት ፅኑ እሥራት እና 2 ዓመት ከሜኖኛውም ህዝባዊ መብቱ እንዲታገድ የቅጣት ውሳኔ ተሰጥቶቷል።
መረጃው፦ የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ዘግቧል።

Amhara Police Commission

11 Nov, 06:53


በኬላ እና ቤት ለቤት በሚደረግ ድንገተኛ ፍተሻ የክላሽን ጥይት እና ሌሎች የወንጀል ድርጊት ፈፃሚዎችን መያዙን ፖሊስ ገለፀ።

በኮምቦልቻ የሃሰና አገር ክፍለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ደረሰ ኑር ሁሴን የተሰጠነን ግዳጅ እና ተልእኮ በብቃት እና በሃቀኝነት በመውጣት የህብረተሰባችንን የሰላም ፍላጎት እውን ለማድረግ ችለናል በማለት የገለፁ ሲሆን የከተማችንን ሰላም እና የህዝባችንን ደህንነት ለማወክ ሊንቀሳቀሱ በሚችሉ ማንኛውም ፀረ-ሰላም ሃይሎች ላይ ህጋዊ እርምጃ በመውሰድ ኮምቦልቻን የህግ የበላይነት የሚከበርባት ከተማ ለማድረግ ተችሏል ብለዋል።

በመሆኑም በርካታ የAKM47 ጠመንጃ ተተኳሽ እና ለወንጀል ተግባር ሊውሉ የሚችሉ ድምፅ አልባ ስለቶችን በፍተሻ መያዛቸውን እና በተለለያዩ ወንጄል ተሳትፈው በቁጥጥር ስር በዋሉ 7 ተከሳችም ላይ አፋጣኝ/RTD/ ከ6 ወር እስከ 3 አመት እስራት ማስቀጣታቸውንም ኢንስፔክተር ደረሰ ተናግረዋል።

ኢንስፔክተር ደረሰ ኑር እንዳሉት ህገወጥ የጦር መሳሪያን ይዘው በተገኙ ፣ በኢንዱስትሪ ፖርኮች ውስጥ ዘልቆ በመግባት ስርቆት በፈፀሙ ፣ የአርሶ አደሮችን የበቆሎ አዝእርት ላይ ውድመት የፈፀሙ እና የባጃጅ ጎማ ይዞው ለመሰወር በሞከሩ ወንጀለኞች ላይ ፖሊስ እጅ ከፍንጅ በማያዝ እና ለፍርድ በማቅረብ ወንጀለኞችን ሊያርም ህብረተሰቡን ሊያስተምር የሚችል ውሳኔ እንደተላለፈባቸው አብራርተዋል።

ስለወንጀል አስከፊነት እና ሰላም ስለማያሰገኛቸው መልካም ቱርፋቶች ከህበረተሰቡ ጋር በግልፅ በመወያየት እና ህበረተሰቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ በክልላችን ያለውን ህገወጥነት እና ስራአት አልበኝነት ያሰከተሏቸውን ዘርፈ ብዙ ማህበራዊ ኢኮኖማያዊና ፖለቲካዊ ምስቅልቅሎችን ህዝባችን አስከፊነቱን እና አውዳሚነቱን ጠንቅቆ እንዲውቅና የሰላም ዘብ እንዲሆነ ሰፊ ሰራወች መሰራታቸውንም እንስፔክተሩ አያይይዘው አስረድተዋል።

ኢንስፔክተር ደረሰ በመጨረሻ በኮምቦልቻ ከተማ እና አካባቢዋ ለፀረ-ሰላም እና ለወንጀለኞች የማትመች የሰላም እና የልማት ከተማ ናት በማለት ገልፀው ህበረተሰቡም እያደረገ ላለው ጉልህ ድርሻ አክብሮታቸውን ገልፀዋል።

Amhara Police Commission

10 Nov, 15:52


"የሁሉ ነገር መሠረት ውስጣዊ አንድነት ነው" ቹቹ አለባቸው (ዶ.ር)

በአማራ ክልል የግጭት መንስኤዎችና የዘላቂ ሰላም ግንባታ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ተካሂዷል።

አውደ ጥናቱን የአማራ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ከአማራ ክልል በጦርነት የተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋምና ግንባታ ፈንድ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ነው ያዘጋጁት፡፡ በአውደ ጥናቱ የክልሉን መሠረታዊ ችግሮች እና የመፍትሔ ሃሳቦች የሚያመላክቱ ጥናቶች ቀርበዋል፡፡

ጥናት ያቀረቡት የአማራ ክልል ሥራ አመራር ኢንስቲትዩት ምክትል ፕሬዝዳንት ቹቹ አለባቸው ( ዶ.ር) የአማራ ክልል ግጭት መንስኤዎቹና መውጫ መንገዶቹ ምን ይኾናሉ ብለን ነው ወደ ጥናት የገባነው ብለዋል፡፡

በጥናት በአጭር ጊዜ የገጠመውን ችግር ከማየት ይልቅ ወደ ኋላ መለስ ብሎ ጉዳዩን በጥልቀት መታየቱን ነው ያመላከቱት፡፡ በአማራ ክልል በየወቅቱ የሚነሳ ችግር መኖሩን ያነሱት ዶክተር ቹቹ በየጊዜው የሚነሳውን ችግር ምክንያት ወደ ኋላ ሄዶ ሥረ ነገሩን መፈተሸ ማስፈለጉን ነው የተናገሩት፡፡

በጥናቱም ችግሮችን የመለየትና የመፍትሔ ሃሳቦችም መቀመጣቸውን ገልጸዋል፡፡ የአማራ ሕዝብን ወደ ችግር የሚያስገቡት ብዙ ምክንያቶች መኖራቸውን ያነሱት ዶክተር ቹቹ አንደኛው ከታሪክ ጋር የሚያያዝ ችግር ነው ብለዋል፡፡ የአማራን ሕዝብ እንደ ጨቋኝ፣ እንደ ገዢ፣ እንደ በዝባዥ የታየበት መንገድ የአማራን ሕዝብ ለጥቃት ሲያጋልጠው ቆይቷል ነው ያሉት።

ፖለቲካዊ ጉዳይ ደግሞ ሁለተኛው ምክንያት ነው። የብሔር እና የአክራሪነት ፖለቲካ ለአማራ ፖለቲካ አይገጥምም፣ ከዚህም ባለፈ እያስጠቃው ነው የመጣው ብለዋል። በሀገሪቱ የብሔር ፖለቲካ የበላይነቱን መያዝ የአማራ ሕዝብ በግጭት አዙሪት እንዲቆይና እንዲቀጥል አድርጎታል ነው ያሉት።

በተከታታይ የሚፈጠሩ ችግሮችን ሊቋቋሙ የሚችሉ ተቋማት አለመኖራቸው ሌላኛው ምክንያት መኾኑን የተናገሩት ዶክተር ቹቹ በተለይም የጸጥታ ተቋማቱ በሚገባቸው ልክ የተደራጁ አለመኾናቸው ችግሩን መግታት እንዳይችሉ አድርጓቸዋል ብለዋል።

የመልካም አሥተዳደር ችግር ሌላኛው ጉዳይ መኾኑን ገልጸዋል። ችግሩ ሕዝቡን እንዲቆጣ እንዳደረገው ነው ያመላከቱት።

የኑሮ ውድነቱ፣ የሥራ አጥነት፣ ሙስና እና የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች ሕዝብን እያስቀየሙ ሁከት የሚፈጥሩ ኃይሎችን የሚደግፉ ሰዎችን እንዲበራከቱ አድርጓል ብለዋል። የአማራ ሕዝብ ችግር መታየት ያለበት ከአምስት እና ስድስት ዓመታት ወዲህ ሳይኾን ከረጅም ጊዜ ጀምሮ መኾኑ አለበት ነው ያሉት።

የአማራን ሕዝብ ከግጭት አዙሪት ለማውጣት የተበላሹ ትርክቶችን ማስተካከል፣ ለአማራ ሕዝብና ለሀገሪቱ የሚመጥን ትርክት መገንባት አለበት ብለዋል። የአማራን ሕዝብ ለጥቃት የዳረገ ትርክት መቀልበስ መቻል አለበት ነው ያሉት። የብሔር ፖለቲካ ለአማራ ሕዝብ አደጋ መኾኑን በተግባር አይተናል ያሉት ዶክተር ቹቹ በሀገሪቱ የብሔር ፖለቲካ የበላይነቱን የሚያጣበትን ትግል ማድረግ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የብሔር ፖለቲካ ገዢ የማይኾንበት፣ ሀገራዊ ትርክት ገዢ የሚኾንበት፣ ሀገራዊ ፖለቲካ የበላይነቱን የሚይዝበት ሥርዓት እንዲፈጠር የአማራ ሕዝብ መታገል አለበት ብለዋል። የአማራ ሕዝብ ከጭቆና የሚወጣው የብሔር ፖለቲካ የበላይነት ሲቀለበስ መኾኑንም አመላክተዋል። ለኢትዮጵያ የሚስማማ ፖለቲካ እስካልተፈጠረ ድረስ የአማራ ሕዝብ እረፍት አያገኝም ነው ያሉት።

ችግሮችን ለመፍታት ጠንካራ ተቋማትን መገንባት ሌላው የመፍትሔ እርምጃ ነው ብለዋል። አሁን ያሉት የጸጥታ ተቋማት እንደገና መሠራት አለባቸው ነው ያሉት። የጸጥታ ተቋማትን በሰው ኃይል፣ በግብዓት በአሠራር እና በአደረጃጀት ማጠናከር እንደሚገባቸውም አመላክተዋል። የመልካም አሥተዳደር ችግሮችን መፍታትም ለክልሉ ሰላም መፍትሔ መኾኑን ነው የተናገሩት።

የአማራ ሕዝብ ውስጣዊ አንድነት ላይ በደንብ መሠራት አለበት ብለዋል። የአማራ ሕዝብ አንድነቱን በማጠናከር ችግሮቹን መፍታት ይጠበቅበታል ነው ያሉት። ለችግሮቹ የጋራ መግባባት እና የጋራ መፍትሔ ማዘጋጀት ይጠይቃል ብለዋል።

የሁሉ ነገር መሠረት ውስጣዊ አንድነት ነው ያሉት ዶክተር ቹቹ ውስጣዊ ችግሮችን ማስተካከል ሳይቻል ውጫዊ ችግሮችን ማስተካከል አይቻልም ነው ያሉት።

Amhara Police Commission

10 Nov, 15:47


ብዝኀነት እና የሕግ የበላይነት ሲከበር ሰላም ይረጋገጣል።

በአማራ ክልል የግጭት መንስኤዎች እና የዘላቂ ሰላም ግንባታ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ላይ ያተኮረ አውደ ጥናት ተካሂዷል።

አውደ ጥናቱን የአማራ ክልል ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ከአማራ ክልል በጦርነት የተጎዱ አካባቢዎች መልሶ ማቋቋም እና ግንባታ ፈንድ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር ነው ያዘጋጁት፡፡

በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የአሥተዳደር ጉዳዮች አሥተባባሪ እና የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኀላፊ ደሳለኝ ጣሰው ክልሉ በሰላም ችግሮች ውስጥ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

የገጠመውን ችግር ለመፍታት ደግሞ መሠረታዊ ምክንያቱን በመለየት መፍትሔውን ማዘጋጀት ይገባል ነው ያሉት።

የአማራ ክልል የባለፉት ዓመታት የቀውስ አዙሪት ምክንያቶች መጠናት እንደሚገባቸው እና መፍትሔ እንደሚያስፈልጋቸው በተሰጠው አቅጣጫ መሠረት መጠናቱን ገልጸዋል።

የአማራ ሕዝብ በለውጡ ሂደት ከፍተኛ ሚና የተጫወተ፣ ዋጋ የከፈለ፣ ሀገሩን የሚወድ፣ አብሮነትን አብዝቶ የሚፈልግ ሕዝብ ነው ብለዋል።

አሁን ያሉ ችግሮች ግን ከአማራ ሕዝብ እሴቶች የወጡ መኾናቸውን ነው የተናገሩት።

በክልሉ ያለው ችግር ግጭቱን በማብረድ ብቻ የሚፈታ አለመኾኑን የተናገሩት ኀላፊው ከዚህ ከፍ ያለ መፍትሔ ይሻል ብለዋል። ታሪካዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች በጥናቱ መነሳታቸውንም ገልጸዋል።

የተደረገው ጥናት ለአማራ ክልል የግጭት አዙሪት መግባት ምክንያቶች እና መፍትሔዎችን ያመላከተ ነው ብለዋል።

ችግሩን ማወቅ አንድ መፍትሔ ነው ያሉት ኀላፊው ችግሩን ከማወቅ ባለፈ ችግሩን መፍታት ወሳኙ ዓላማ ነው ብለዋል። ችግሩን ለመፍታት የአምስት ዓመታት ስትራቴጂክ ዕቅድ መታቀዱንም ገልጸዋል።

የሰላም እና ጸጥታ ጉዳይ የአንድ ተቋም ብቻ አለመኾኑንም ተናግረዋል። ለመፍትሔው የሁሉንም ድርሻ ይጠይቃል ነው ያሉት። ሰላም ከአንድ ወገን የሚመነጭ አይደለም፣ ሰላም ሁለንተናዊ ገጽታ አለው ብለዋል።

ሰላም ከሌለ የማኀበራዊ፣ የምጣኔ ሃብታዊ እና የፖለቲካዊ ተጠቃሚነት እንደማይኖርም ገልጸዋል።
ሰላም ለሕዝብ ያገባኛል የሚሉ ሁሉ ሊሳተፉበት የሚገባ ጉዳይ ነው ብለዋል። የብዙዎች ሃሳብ ተደምጦ፣ ብዝኀነት እና የሕግ የበላይነት ሲከበር ነው ሰላም የሚረጋገጠው ነው ያሉት።

ሰላም ከጸጥታ ተቋማት በተጨማሪ በሕዝብ ተሳትፍ የሚፈታ ስለመኾኑም አመላክተዋል። ሁሉም ለሰላም ግንባታ መሥራት አለበትም ብለዋል። የሰላም ፋይዳ እና ትርጉም ለሁሉም ሰው መኾኑንም ገልጸዋል።

በሰላም እጦት በርካታ ነገሮች መታጣታቸውን የተናገሩት ኀላፊው በራሱ ክልል እና ሀገር ነጻነት ያጣ ማኅበረሰብ መኖሩን ነው የገለጹት። ይሄን መፍታት ደግሞ ይገባል ብለዋል። ጥናቱ ዕውን እንዲኾን ሁሉም መተባበር እንደሚገባው ነው ያስገነዘቡት።

Amhara Police Commission

10 Nov, 13:52


የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ዘመኑን የሚመጥን የቴክኖሎጅ እና የሰው ኀይል አቅም በመገንባት የወንጀል መከላከል አቅሙን አጎልብቷል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በአዲስ አበባ ዋናው መሥሪያ ቤት ከፍተኛ ወጭ የተደረገበት የሆስፒታል ማስፋፊያ ሕንጻ ገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ማድርጉን አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ የመሥሪያ ቤቱን ሕንጻ ምርቃት እንዲኹም የ2016 በጀት ዓመት የማጠቃለያ እና የምሥጋና መርሐ ግብር አካሂዷል።

በፕሮራሙ የተገኙት የአሥተዳደር እና ልማት ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል ነብዩ ዳኘ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በ2016 በጀት ዓመት የሪፎርም ሥራዎችን በማዘመን ውጤታማ ተግባራት ማከናወኑን አንስተዋል።

የዜጎችን ሰላም እና ደኅንነት ከማረጋገጥ ባሻገር ማኅበራዊ አገልግሎት የሚሰጡ ግዙፍ የሕክምና ተቋማትንም እየገነባ ነው ብለዋል።

በአዲስ አበባ ዋናው መሥሪያ ቤት የተገነባው የሆስፒታል ማስፋፊያ ሕንጻ ለአገልግሎት ክፍት መኾኑን የገለጹት ጄኔራሉ ሕንጻው በውስጡ 165 ክፍሎች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡ ይህም ከአሁን በፊት በተቋሙ ያጋጥም የነበረውን የሕክምና አገልግሎት አሰጣጥ ችግር የሚፈታ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ተቋሙ የሎጀስቲክ፣ የቴክኖሎጅ እና የሰው ኀይል አቅምን በመገንባት የወንጀል መከላከል እና ምርመራ አቅሙን ማጎልበት ተችሏል ብለዋል።

ዘመኑን የሚመጥን የሎጅስቲክ አቅምን በማጎልበት፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጅን በመጠቀም፣ እንዲኹም የሠለጠነ የሰው ኀይል በማፍራት የዜጎችን ሰላም እና ደኅንነት እየጠበቀ እንደኾነም ነው ያብራሩት።

ሀገራዊ ተልዕኮን በመወጣት እንዲኹም ከውስጥ እና ከውጭ ካሉ ባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ግንኙነት በማጠናከር ተጨባጭ እና አበረታች ተግባራት መፈጸሙንም ነው ያነሱት።

ተቋሙ በኢትዮጵያ ብሎም በምሥራቅ አፍሪካ ግዙፍ የሕክምና ተቋማትን በመገንባት ለሀገር ውስጥ እና በውጭ ላሉ የሠራዊት አባላት የሕክምና አገልግሎት ለመሥጠት እየሠራ ነው ተብሏል።

በዕለቱ በ2016 በጀት ዓመት የተሻለ የሥራ አፈጻጸም ለአስመዘገቡ ተቋማት እና ባለሙያዎች ምሥጋና እና ዕውቅና ተበርክቷል።

በመርሐ ግብሩ የኢትዮጵያ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዦች፣ መኮንኖች፣ የማኔጅመንት አባላት እንዲኹም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

Amhara Police Commission

03 Nov, 16:26


ከ29 ሚሊዮን ብር በላይ ለመውረስ የሞከሩ ግለሰቦች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋሉ።

የሰሜን ወሎ ዞን ነዋሪ የሆነው ግለሰብ በሀሰት ራሱን ወ/ተክለኀይማኖት አድማሱ እባላለሁ በማለት በሰሜን ወሎ ዞን ቆቦ ከተማ 01 ቀበሌ ነዋሪ የነበረን የሟች አድማሱ ምረቱ ልጅ ነኝ በማለት በሟች አካውንት የሚገኝን 29,115,665(ሃያ ዘጠኝ ሚሊየን አንድ መቶ አስራ አምስት ሽህ ስድስት መቶ ስልሳ አምስት ብር) ለመውረስ ሞክሮ ድርጊቱ ከሽፎበታል።

ለዚህ የማጭበርበር ተግባሩም ሁለት የሀሰት ምስክሮችን በወረዳ ፍርድ ቤት በማቅረብ በሀሰት አስመስክሮ ለንግድ ባንክ ደብዳቤ በመፃፍ ብሩን ለማውጣት ይሞክራል።

ጉዳዩ በጥቆማ የደረሰው ፖሊስም ሁለቱ በሀሰት የመሰከሩ ግለሰቦችንና ጉዳዩን ሲያመቻች የነበረውን አቶ ሙሀመድ ይማም የተባለ የሀብሩ ወረዳ ወጣትና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊን በቁጥጥር ስር በማዋል አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት ላይ ይገኛል።

Amhara Police Commission

01 Nov, 06:53


የስርቆት ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በፅኑ እስራት ተቀጣ።

ተከሳሽ አስቻለው የኔዓለም የተባለ ግለሰብ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 አካባቢ በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 16 ልዩ ቦታው ህፃናት ኦፕሪስ የተባለ አካባቢ የዉሃ ፓምፕ እና የላሜራ ብረት ከ30ኪ.ግ ሚስማር ጋር በመዝረፍ ኮድ 1 ሰሌዳ ቁጥር 75329 በሆነች ባጃጅ ጭኖ ለመሄድ ሲሞክር በቁጥጥር ስር ውሏል።

ምርመራውም በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ  በ6ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ወንጀል ምርመራ ክፍል ተጣርቶ ለሚመለከተው የፍትህ አካል ተላከ።

የምርመራ መዝገቡ የደረሰው የባህርዳር ዙሪያ ወረዳ ፍ/ቤትም ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ግለሰቡ በ4 ዓመት ፅኑ እስራት እንድቀጣ ወስኖበታል።

Amhara Police Commission

31 Oct, 12:42


ተዘርፎ የነበረን ጤፍ በማስመለስ ለባለቤቱ ማስረከቡን ፖሊስ ገለፀ።

በታጣቂዎች ተወስዶ ታግቶ የነበረን ንብረትነቱ የአቶ ዋጋነህ መንግስቴ የሆነን የጭነት መኪና እስከጫነው 250 ኩንታል ጤፍ ማስመለሱን የበባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ7ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።

እንደ ጣቢያው የወንጀል ምርመራ ክፍል ኀላፊ ኢንስፔክተር ክንድየ ይማም ገለፃ ተሽከርካሪው ጥቅም 10 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9:30 አካባቢ 250 ኩንታል ጤፍ በመጫን ለንግድ ስራ ከደቡብ ጎንደር ዞን አንዳቤት ወረዳ ወደ ባህርዳር እየተጓዘ እያለ ባህርዳር ዙሪያ ወረዳ ሮቢት ባዕታ ላይ ሲደርስ በታጠቁ ሀይሎች ተይዞ ሹፌሩን እና አብረው የነበሩ ግለሰቦችን በመያዝ ወደማይታወቅ ስፍራ ይዘዋቸው ይሄዳሉ።

ኢንስፔክተር ክንድየ እንደሚሉት ተሽከርካሪውን ከነጤፉ ወደ ባህርዳር ከተማ አፄ ቴዎድሮስ ክ/ከተማ በራሳቸው ሹፌር በማምጣት ማራኪ ቀበሌ ልዩ ቦታው ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን አቃኔ አድማሴ ከተባለ ግለሰብ አንድ መጋዘን ውስጥ ጤፉን በማራገፍ መኪናውን እዛው አካባቢ ታርጋውን በመፍታት ያስቀምጡታል።

ፖሊስም የደረሰውን ጥቆማ መሰረት አድርጎ መኪናውን ካገኘ በኃላ የአካባቢውን መጋዘን ሲፈትሽ ጤፉን ሊያገኘው ችሏል ይላሉ ኢንስፔክተር ክንድየ ይማም ከጉዳዩ ጋር በተያያዘም ባለ መጋዘኑን ጨምሮ አራት(4)ግለሰቦችን በቁጥጥር ስር በማዋል አስፈላጊውን ምርመራ በማጣራት ለሚመለከተው የፍትህ አካል መላኩን ኢንስፔክተር ክንድየ አክለው ገልጸዋል።

Amhara Police Commission

31 Oct, 12:36


በወቅታዊ የሰላምና የፀጥታ ጉዳይ ዙሪያ ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር ውይይት ተካሄደ።

በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ከአፄ ቴዎድሮስ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች ጋር በወቅታዊ የሰላም እና የፀጥታ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት ማድረጉን በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ7ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።

የጣቢያው የህዝብ ግንኙነት ክፍል መረጃ እንደሚያመላክተው በክፍለ ከተማው ከሚገኙ የኃይማኖት አባቶቾ፣የቆሎ ተማሪዎችን ጨምሮ ከሸንበቆዱር፣ከኩርቢ፣ከገድሮ፣ከዘንዘልማ እና ከሰሳበረት ቀጠና ነዋሪዎች ጋር ሰላምን በጋራ ማረጋገጥ እና እየተፈፀሙ ባሉ ወንጀሎች ዙሪያህብረተሰቡ ለፀጥታ ሀይሉ አጋዥ በሚሆንባቸውና ጉዳዮች እና በመሳሰሉት ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

በተመሳሳይ በማራኪ ቀበሌ ከሚገኙ ዘንባባና ፀደይ አፀደ ህፃናት ትምህርት ቤት ለሚገኙ የተማሪ ወላጆችም የቀጠናውን ሰላም ለማረጋገጥና ለሚፈጠሩ ወንጀሎች መረጃ ጂስጠት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት መደረጉን በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የ7ኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ያደረሰን መረጃ ያመላክታል።

Amhara Police Commission

31 Oct, 12:32


በክልሉ የተከሰተውን የሰላም መደፍረስ ወደነበረበት ለመመለስ የክልል ተቋማት የስራ ኃላፊዎች የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል ተባለ፡፡

“ሠላም ለሁሉም፣ሁሉም ለሠላም” በሚል መሪ ሀሳብ ከክልል ተቋማት ዳይሬክተሮችና ቡድን መሪዎች ጋር የሠላም ኮንፈረንስ በባህርዳር ከተማ ተካሂዷል፡፡

በኮንፈረሱ የተገኙት የአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካና ርዕዮት-አለም ዘርፍ ኃላፊ ዘሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) እንዳሉት የሠላም ትርጉሙ የሚታወቀው ሠላም ሲደፈርስ ነው፡፡ ይህንንም በክልላችን ባለፈው አንድ አመት በተግባር አይተነዋል፡፡

ሠላም ለሰው ልጆች ፍላጎት መሻት ዋስትና በመሆኑ ከምንተነፍሰው አየር ባልተናነሰ ሁኔታ ከፍ ያለ ዋጋ አለው ብለዋል፡፡

ዘሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) አክለውም ግጭት በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና፣ በማህበራዊ መስኮች እጅግ አደገኛ ጥፋትን ያስከትላል፤ ግጭት ሰውና ሀብትን ከማውደሙ በተጨማሪ በትውልዶች መካከል ከፍተኛ ክፍተትን ይፈጥራል፡፡

አሁን ላይ ካለው የግጭት አዙሪት ለመውጣት በክልላችን ዘርፈ ብዙ ስራዎችን ስንሰራ ቆይተናል፡፡ በዚህም በክልሉ በሁሉም ቦታዎች ውጤታማ ስራዎችን ለማስመዝገብ በቅተናል ያሉት ኃላፊው ለዚህ ውጤት መመዝገብ ደግሞ ህብረተሰቡ በባለቤትነት እና በእኔነት ስሜት ስራዎችን በአግባቡ መስራት በመቻሉ ነው ብለዋል፡፡

የዚህ የሰላም ኮንፈረንስ በክልል ደረጃ መካሄዱ ዋና አላማው፣ በባለፈው አመት የመጣንባቸውን ምዕራፎች በጥልቀት በመገምገም፣ በቅርቡ የተጀመሩትን ሁሉን አቀፍ ሰላም በክልላችን የማረጋገጥ ስራ በማጠናከር ሚናችንን እንደየ ኃላፊነታችን እንድንወጣ ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

መድረኩን የኢፌዴሪ የጦር ኃይሎች ም/ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ
እና በአማራ ክልል ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የፖለቲካና ርዕዮት-አለም ዘርፍ ኃላፊ ዘሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) መርተውታል፡፡

በክልሉ ይህን መድረክ ጨምሮ 41 የሰላም ኮንፈረስ መድሮኮች እንደሚካሄዱ ዘሪሁን ፍቅሩ(ዶ/ር) ጠቁመዋል፡፡

Amhara Police Commission

30 Oct, 17:03


ጥንቃቄ ለትራፊክ አደጋ

ጥቅምት 18 ቀን 2017 ዓ/ም ከጥዋቱ 2:00 ስዓት አካባቢ በቻግኒ ከተማ አስተዳደር 05 ቀበሌ በተቃራኒ አቅጣጫ የሚጓዙ ባለሶስት እግር/ባጃጅ ተሽከርካሪዎች በመጋጨታቸው አንድ ሞት አንድ ከባድ ጉዳት እንዲሁም ሁለት ቀላል ጉዳት መድረሱን የቻግኒ ከተማ አሰተዳደር ፓሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።
የመረጃው፦የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ፖሊስ መምሪያ ነው።

Amhara Police Commission

30 Oct, 16:42


ትጥቅ ይዞ ኮብልሎ የነበረ የፖሊስ ባልደረባ የእስራት ቅጣት ተወሰነበት።

በዋግኸምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን የአበርገሌ ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት የሲቃላ ቀጠና አስተባባሪ የነበረው ሳጅን አበባው ገብሩ ከ2010 ዓ/ም ጀምሮ የፖሊስ ተቋምን ተቀላቅሎ ለ6 አመት ገደማ በተቋሙ የሰራ ቢሆንም መንግስት እና ህዝብ የጣለበትን አደራ ወደ ጎን በመተው የፈፀመውን ቃለ-መሀላ በማፍረስ ሰኔ 08 ቀን 2016 ዓ/ም ከነ ጦር መሳሪያው ከድቶ(ኮብልሎ )ከአካባቢው ተሰውሮ ቆይቷል።
ተጠርጣሪው የተለያዩ ቦታዎችን ቢቀያይርም በተደረገ ትስስርና ክትትል ነሀሴ11/2016 ዓ/ም ሰሜን ጎንደር በየዳ ወረዳ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
አባሉ ምንም እንኳን ጦር መሳሪያው በተከዜ ወንዝ ተወሰደብኝ ብሎ ሊያጭበረብር ቢሞክርም በምርመራ ሂደቱ መሸጡን ገዥና አሻሻጩን በቁጥጥር ስር በማዋል የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት አረጋግጦበታል።

ፖሊስ የፍሬ ነገሩን ዳና በመከተል ጦር መሳሪያው መጀመሪያ ከተሸጠበት አበርገሌ ወረዳ 015 ደቢ በለቃ ቀበሌ ከዚያም ሰሜን ጎንደር ጠለምት ወረዳ ለ3ኛ ጊዜ በየዳ ወረዳ ከተሸጠለት ግለሰብ በመከታተል ና.ቁ 6023 ማይካ ኮፍ ክላሽንኮቭ ጦር መሳሪያን በቀን 03/13/2016 ዓ.ም የአበርገሌ ወረዳ ፖሊስ ንብረቱን መረከብ ችሏል።
ፖሊስ ምርመራውን በበቂ ማስረጃዎች አጠናቆ ለወረዳው ዐቃቤ ህግ ከላከ በኋላ በተገቢው የህግ አግባብ የቀረበውን የክሶ መዝገብ የተመለከተው የዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አሰ/ር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የወንጀል ህጉን አንቀፅ 288(1) በመተላለፍ እና የሙስና ወንጀሎችን ለመደንገግ በወጣው አዋጅ ጥቁር 881/2007 ዓ.ም አንቀጽ 31(2) በመተላለፍ ከባድ ዕምነት ማጉደል ተከሳሹ ሳጅን አበባው ገብሩ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ እሱንም ያርማል ሌሎችን ያስተምራል በማለት ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም ባስቻለው ችሎት በ5 ዓመት ፅኑ እስራትና በ5000(አምስት ሽሕ ) ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጣ ወስኖበታል ሲል ከዋግኸምራ ብሄ/አስ ፖሊስ የህ/ግንኙነት ዋና ክፍል ኀላፊው ም/ኮማንደር ደሳለኝ ጌታሁን መረጃውን አድርሶናል።

Amhara Police Commission

28 Oct, 12:40


ተማሪዎች የትራፊክ አደጋ ሰለባ እንዳይሆኑ የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን የ4ኛ ፖሊስ ጣቢያ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ገለጸ ።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በንጉስ ተክለሀይማኖት ክፍለከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከአደጋ ተጋላጭነታቸው አንጻር በመለዬት ተማሪዎች የትራፊክ አደጋ ሰለባ እንዳይሆኑ የሚያስችል የግንዛቤ ማስጨጥ ትምህርት በሁሉም ትምህርት ቤቶች እየተሠጠ መሆኑንን የጣቢያው የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ክፍል ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር አበባው አየለ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጸዋል ።

የግንዛቤ ማስጨበጥ ትምህርቱ በዋነኝነት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው በሚመጡበት እና በሚመለሡበት ግዜ እንዲሁም ማህበራዊ አገልግሎቶችን ለመፈጸም መንገድን ተጠቅመው በሚጓዙበት ግዜ እግረኛ መንገድ ባለበት በእግረኛ መንገድ እንዲጓዙ እና የእግረኛ መንገድ በሌለበት የመንገዱን የግራጠርዝ ይዘው እንዲጓዙ እንዲሁም መንገድን በዜብራ መስመር ግራ እና ቀኝ አይተው እንዲያቋርጡ እና ሌሎች ከእግረኛ አንፃር ተማሪዎች ሊያደርጓቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎችን በትምህርቱ ተካተው መሠጠቱን ተናግረዋል ።
በተለይ የትራፊክ መጨናነቅ በሚበዛባቸው ሰዓቶች እና ቦታዎች ፣ደሴት አካባቢ ፣የትራፊክ መብራት አካባቢ በልዩ ትኩረት እና ጥንቃቄ መንገዱን ሊጠቀሙ እንደሚገባ አስረድተዋል ።

በክፍለ ከተማው በሚገኙ ከአደጋ ተጋላጭነታቸው አንጻር በቅደም ተከተል የግንዛቤ ማስጨበጥ ስራው እየተሰጠ መሆኑን ተናግረው ይህን ተግባር በማስፋት በሁሉም ትምህርት ቤቶች ለማዳረስ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን ገልጸዋል ።

ተማሪዎች የትራፊክ አደጋ ሠለባ እንዳይሆኑ ቤተሰብ እና መምህራን ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት ከሚመለከታቸው አጋር አካላት ጋር በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቁመዋል ።

በቀጣይ የተማሪ ትራፊክ ክበብ አባላትን መልምሎ በማሰልጠን ወደ ስራ ለማስገባት በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ጨምረው ገልጸዋል።

የትራፊክ አደጋ የሁላችንም ቁልፍ ችግር በመሆኑ በመከላከል ስራው ላይ ሁሉም ማህበረሰብ ክፍል በሀላፊነት ስሜት ሊሰራ እንደሚገባ አሳስበዋ ።
የደብረማርቆስ ከተማ ፖሊስ ህዝብ ግንኙነት ነው።

Amhara Police Commission

28 Oct, 08:44


በምዕራብ ደምቢያ ወረዳ ከዳህና ዋዋ ቀበሌ ነዋሪዎች ጋር ህዝባዊ የሰላም ዉይይት ተካሄደ።

በዉይይቱ የ502ተኛ ኮር ምክትል አዛዥና የደምቢያ ቀጠና መከላከያ ሰራዊት አስተባባሪ ኮሎኔል በየነ አጋን ጨምሮ የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር የፀዳዉ ምስጋናዉን ጨምሮ የቀበሌዉ ነዋሪዎች እና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

በዕለቱ መልእክት ያስተላለፉት የመከላከያ ሰራዊት አስተባባሪው ኮሎኔል በየነ አጋ ይህ ዘራፊና ጽንፈኛ ቡድን በአማራ ህዝብ ስም እየነገደ ያለና ህዝቡም እንደማይጠቅመዉ አዉቆ አሁን መንግስት የጀመረውን ህግ የማስከበርና ዘላቂ ስላም የማምጣት ስራን አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ተናግረዋል።

በመሆኑም ህብረተሰቡ ከመንግስትና ከሰራዊቱ ጎን በመሆን የበኩሉን ሊወጣ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል የወረዳው ፓሊስ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ምክትል ኢንስፔክተር የፀዳዉ ምስጋናዉ በበኩላቸው በዳህና ዋዋ ቀበሌ ስለ ሰላም የህዝብ ዉይይት ለማካሄድ ጥምር ጦሩ ከቀበሌዉ እንደደረሰ ጽንፈኛዉ ቡድን ተኩስ ቢከፍትም ጥምር ጦሩም ህዝብና ተቋማትን በማይጎዳ መልኩ ወታደራዊ ጥበቡን ተጠቅሞ ቁስለኞችንና ምርኮኞችን መያዛቸውን ገልፀዋል።

በዚህም የተያዙ ቁስለኞችና ምርኮኞችን ወደ ወረዳዉ በማምጣት ህክምና እንዲደረግላቸዉና ዉሃና ምግብ በማቅረብ በህግ ጥላ ስር እንደሚገኙ አስረድተዋል።

በመጨረሻም የተማረኩና ቆስለዉ የተያዙ የጽንፈኛዉ ቡድን አባላት በበኩላቸዉ መከላከያ ከያዛችሁ ይረሽናችኋል እየተባለ ሲነገር ነበር የቆየ አሁን ግን በተባለው ልክ አይደለም ያገኘናቸዉ እጅ ስንሰጥ ምንም ጥይት ሳይተኮስብን፣ሳንገላታ የቆሰልነዉም በፍጥነት ወደ ህክምና በመድረስ ምግብና ዉሃ ቀርቦልን በጥሩ ሁኔታ ላይ እንገኛለን ብለዋል።

መረጃው የወረዳው ኮሙኒኬሽን ነው

Amhara Police Commission

27 Oct, 06:27


ሰላምን ለማፅናት ህዝባዊ ውይይት ተካሄደ።

በአየሁ ጓጉሳ ወረዳ አየሁ ቀበሌ እና ድኩና ደረብ ቀበሌ ከማህበረሰቡ ጋር በወቅታዊ አካባቢያዊ ሁኔታ ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል።
የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰላምና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢሻው የእርሻና የአካባቢውን ማህበረሰብን አወያይተዋል ።
በውይይቱ የተገኙት የአካባቢው ማህበረሰብ መንግስት የህግ ማስከበር ዘመቻውን አጠናክሮ እንዲቀጥልና ተማሪዎች እንዲማሩ ፣ የታመመ እንዲታከም ጤና ጣቢያው አገልግሎት መስጠት እንዲጀምር ጠይቀዋል።
መረጃው የአየሁ ጓጉሳ ወረዳ የመንግስት ኮሚኒኬሽን ነው።

Amhara Police Commission

24 Oct, 09:24


በደሴ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ፍርድ ቤት ዳኛ በነበሩት በአቶ ሙሉጌታ ከበደ ግድያ ዙሪያ ከምርመራ ቡድኑ የተሰጠ ማብራሪያ

የደሴ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ በተዋቀረው የምርመራ ቡድን ከዚህ በፊት ለማህበረሰቡ ስለግድው ማብራሪያ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

ስለዚህ የምርመራ ቡድኑ ያለበትን ሁኔታ ለማህበረሰቡ እንደምናሳውቅ የገለጸ ሲሆን ምንም እንኳን የግድያ ወንጀሉ በባህሪው ውስብስብ ቢሆንም የምርመራ ቡድኑ ደከመን ሰለቸን ሳይል ሌት ከቀን አሁንም በመስራት ላይ ይገኛል፡፡

ምርመራውን ይበልጥ ለማጠናከር በቡድኑ ውስጥ ተጨማሪ የምርመራ ቡድኑ የተዋቀረ ሲሆን በቡድኑም የፌደራል ፖሊሲ መርማሪ፣የጠቅላይ አቃቤ ህግ ፣ የዞንና የከተማ አቃቤ ህግ ተጨምረውበት ምርመራው እያጣሩ ይገኛሉ።
በእስካሁኑ የምርመራ ሂደት በድርጊቱ የተጠረጠሩ ግለሰቦች የተያዙ ሲሆን ከተጠርጣሪዎቹ ተጨማሪ የታክቲክ እና የቴክኒክ ማስረጃዎችን ማሰባሰብ ተችሏል፡፡
የምርመራ ቡድኑ ምርመራው ሙሉ ለሙሉ ያላጠናቀቀ በመሆኑ ለሰላም ወዳዱ ማህበረሰባችን በቀጣይ የምርመራውን የመጨረሻ ውጤት የሚያሳውቅ መሆኑን የምርመራ ቡድኑ እየገለፀ ህብረተሰቡ በተለመደው ትዕግስቱ እንዲጠብ ማሳሰብ እንወዳለን ሲል የመርምራ ቡደኑ ገልጿል።
የደሴ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት

Amhara Police Commission

24 Oct, 07:28


የፀረ-ሰላም ቡድን መረጃወችን ጨምሮ በህዝብ እና በመንግስት አገልጋሎት ሰጭ ተቋማት ላይ ዝርፊያ የፈፀሙ ግለሰቦችን መያዙን የኮምቦልቻ ፖሊስ ገለፀ።

በኮምቦልቻ የአቢሻ አገር ክፍለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር ውሴን መብራቱ እንደገለፁት በክፍለ ከተማቸው ፖሊስ ሰራዊት ከህበረተሰቡ ጋር እና ከሌሎች አጋር የፀጥታ ሃይል ጋር በመሆን ስራወችን በበለጠ ውጤታማነት እየሰሩ መሆኑን ገልፀው በዚህ ሳምንት ብቻ 4የፀረ ሰላም ቡድን ተላላኪ ናቸው ያሏቸውን በቁጥጥር ስር አውለው ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢንስፔክተሩ አስከትለውም በተሰጣቸው የክፍለ ከተማ ክልል ውስጥ ድንገተኛ ፍተሻ እና ጠንካራ የኬላ ክትትል በመደረጉ ንብረትነቱ የህዝብ እና የመንግስት በሆነ የኤሌክትሪክ ግልጋሎት ሰጭ ተቋም ላይ ውድመት የፈጠሩ ወንጀለኞችንም ይዞ መርመራ መጀመሩን አስታውቀው በተመሳሳይ ህጋዊ ባልሆነ መልኩ ሲዘዋወር የነበረም የአፈር ማዳበሪያ ከነተጠርጠሪወቹ በቁጥጥር ስር ሊውል መቻሉን አዛዡ ተናግረዋል ።

ኢንስፔክተር ውሴን አክለውም የወጣቱን የስራ ሞራል ሊጎዱ በሚችሉ እና የተለያዩ ወንጀለኞች መደበቂያ ናቸው ብለው ባሰቧቸው አልባሌ መዋያወችን እና መገልገያ የሽሻ እቃወችንም መያዛቸውን አስረድተው በጉዳዩ ላይ ተሳታፊ በነበሩት ግለሰቦች ላይም በደንብ እና በመመሪያው መሰረት ቅጣት እንደተወሰነባቸው አብራርተዋል ።

በመጨረሻም በክፍለ ከተማቸው ህዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠር አካባቢው ለፀረ ሰላም ሃይሎች እና ለወንጀለኞች አመች በማይሆን መልኩ ሰራ እየተሰራ እንደሆነ የገለፁ ሲሆን ሰላም ወዳድ ለሆነው የኮምቦልቻ ህዝብም አክብሮታቸውን ገልፀው እነዚህን እና መሰል ተልዕኮወች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም አስታውቀዋል።

Amhara Police Commission

23 Oct, 07:51


በከሚሴ ከተማ አስተዳደር የትራፊክ ቁጥጥሩን ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
ለትራፊክ ፖሊሶችና አጋዥ ሀይሎች አንፀባራቂ የአልባሳት ድጋፍ ተደርጓል፡፡

የኦሮሞ ብሄረሠብ አስተዳደር መዲና የሆነችዉ ከሚሴ ከተማ ያላት መልካምድር አቀማመጥ ሜዳማ ነዉ ስለሆነም በተለይ አሽከርካሪዎች በፍጥነት ማሽከርከርን በመምረጣቸዉ በከተማዋ ለሚከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች መንሰኤ እየሆኑ ይገኛሉ፡፡በፍጥነትና በሌሎች ምክንያቶች የሚደርሱ አደጋዎችን ለመከላከልና ለመቀነስ ባለድርሻ አካላት ጥረት በማድረግ ላይ ናቸዉ፡፡

በከሚሴ ከተማ ከሚገኙ ዘጠኝ ት/ቤቶች ከእያንዳዳቸዉ አስር አስር ተማሪዎችን አጋዥ የትራፊክ ፖሊሶችን በማሰልጠን ወደ ስራ ማስገባቱን በከተማ አስተዳደሩ ፖሊስ ፅ/ቤት የመንገድ ደህንነት ትራፊክ ቁጥጥር ክፍል ሀላፊ ኢንስፔክተር ትዝብት አባቡ ገልፀዋል፡፡የመናኸሪያ ዉስጥ የሚሠሩ ግለሠቦችና በበጉ አድራጉት ስራ የተሠማሩ ግለሠቦችም የትራፊክ አደጋን ለመከላከል የዜግነት ድርሻቸዉን እየተወጡ እንደሚገኙም ኢንስፔክተሯ አስረድተዋል፡፡

የትራፊክ ማስተናበር ስራዉ ስኬታማ እንዲሆንና ከአደጋ የፀዳ ሠላማዊ የትራፊክ እንቅስቃሴ እንዲኖር ከተማ አስተዳደሩ ከመንገድ ትራንስፖርት ፅ/ቤት ጋር በመተባበር ግምታቸዉ ከ60ሽ ብር በላይ የሚሆኑ ሁለት መቶ አንፀባራቂ የትራፊክ አልባሳት ድጋፍ ማድረጉን ሀላፊዋ ተናግረዋል፡፡ይህም የትራፊክ ፖሊሶችን ጨምሮ ለተማሪ ትራፊኮች፣ለመናኸሪያ ዉስጥ ሠራተኞች፣በትራፊክ በኩል በበጉ አድራጉት ስራ ለሚያገለግሉ የህብረተሠብ ክፍሎች እንዲደርስ ተደርጓል፡፡

በተለይ አጋዥ ሀይሎቹ አልባሳቱን እንዲለብሱ መደረጉ ከሌላዉ ህብረተሰብ ተለይተዉና ደምቀዉ በመታየታቸዉ የትራፊክ ማስተናበር ስራዉን በማቀላጠፍ ከፍተኛ ሚና እንዳለዉ የገለፁት ኢንስፔክተር ትዝብት የአልባሳት ድጋፍ ያደረጉትን ከተማ አስተዳደሩንና መንገድ ትራንስፖርት ፅ/ቤትን በፖሊስ ጣቢያዉ ስም አመስግነዋል፡፡

Amhara Police Commission

20 Oct, 13:33


የደብረታቦር ከተማ መናሀሪያ ውስጥ የሚታየውን ችግር ለመቅረፍ እየተሰራ ነው።

በከተማ አስተዳደሩ በሚገኘው መነሀሪ የሚፈጠረውን ወከባና መጨናነቅ ለመቅረፍ ስራዎች እየተሰሩ ነው። በተለይ ተሳፋሪዎችን ማንገላታትና በማዋከብ ለስርቆት እንዲዳረጉ የማደረግበትን አግባብ ለማረም ሹፌሮች እና ረዳቶች ውጭ ማንም እንዳይገባ ለዚህም በውይይት ህብረተሰቡ የሚለየው አለባበስና መለያ እንዲኖራቸው ተደርጓል።

Amhara Police Commission

20 Oct, 13:32


ወንጀሎች ከፖሊስ የበለጠ ለማህበረሰቡ ቅርብ ናቸው።

ከመነቃቀፍ መደጋገፍን፣ከመናናቅ መከባበርን፣ከመገፋፋት መተባበርን፣ከመጥፎ ጥሩን፣ከጥል ፍቅርን፣ከእኔነት እኛነትን፣ከመራራቅ መቀራረብን፣ከመለያየት አንድነትን፣ከመገዳደል መዋደድን፣ከመግደል ማዳንን፣ከግጭት ሰላምን-በማስበለጥ ለራሳችንም ለህዝባችንም የተሻለውን በማድረግ ግላዊ ሀላፊነትን በመወጣት ማህበረሰባዊ መብትን ማክበር ይኖርብናል።

ከማፍረስ መጠገንን፣ከመናድ መካብን፣ከውድቀት ስኬትን፣ከሰቆቃ እርጋታን፣ከመተቻቸት መግባባት፣ከጭቆና ነፃነትን፣ከብቸኝነት አብሮነትን፣ብናስቀድምስ?

"ፀሀይ የሞቀውን ሰው ሳያውቀው አይቀርም።"ይሉት ሀገራዊ ብሂል ምንም ወንጀል፣ምንም ሚስጢር ከማህበረሰቡ አይሰወርምና የሚፈፀሙ ወንጀሎችም ጎጂነታቸው ራሱን ማህበረሰቡን በመሆኑ መከላከል ካልቻልን ለፀጥታ ሀይሉ አጋዥ መሆን ትርፉም ለኛ አትራፊውም እኛው ነንና ትኩረት ብንሰጠውስ?

ፅድቅና ኩነኔ ቢኖርም ባይኖርም፣
ከክፋት ደግነት ሳይሻል አይቀርም።
እንዲሉ"ጥሩ መሆን ዋጋ ካላስከፈለ መጥፎ መሆን ለምን አስፈለገ።"ከህዝባችን በግደታ የተዘረፈን ሰላም መመለስ ግድ ይሆንብናል።ከእገታ እስከ ዝርፊያ፣ከመፈናቀል እስከ ግድያ አያሌ በደሎችን የተሸከመው ማህበረሰባችን በምን እዳው ነው?ለችግሩ ሰበብ የሆነ አካልስ ትርፉ ምኑ ጋር ነው? ከተንኮለኛነትና ወንጀለኛነት መፅዳት መቻል ቀጠሮ የማይያዝለት ጉዳይ ነው።

ሰላምን መፈለግ ብቻውን ሰላም አያስገኝም።መዋኘት እየፈለግክ መርጠብን ከፈራህ የሚዋኙ ሰዎችን እያዩ መቅናት ነው የሚሆነው።

ከክልል ባልተሻገረ፣ከቀበሌ ባላለፈ፣ከጎጥ ባልተራመደ፣ጠበብ እስተያየት የራስን ወገን መጨቆን፣የራስን ህዝብ ሰላም ከመንሳት በአርቆ አሳቢነትና በሁሉን አቀፍ ሚዛናዊ መነፀር ሁሉን ማየት ትርፍ እንጂ ኪሳራ የለውም።

የሚፈፀሙ ወንጀሎችም ከፖሊስ የበለጠ ለማህበረሰቡ ቅርብ ናቸው ስለሆነም በማጋለጥ፣በመቆም ሰላማችንን በጋራ መጠበቅ ኀላፊነታችን ፣ልማታችንን በህብረት ማስቀጠልን ልምዳችን ማድረግ ይኖርብናል።

Amhara Police Commission

15 Oct, 07:08


በመተከል ዞን እና በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አዋሳኝ አካባቢዎች ያለውን ሰላም ለማስከበር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ የጋራ ውይይት ተካሄደ።

በአማራ ክልል አዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን እና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን አዋሳኝ አካባቢዎች የሚስተዋሉ ችግሮችን በጋራ ለመከላከል ያለመ ውይይት በግልገል በለስ ከተማ ተካሂዷል።

የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ መኮንኖች፣ ከፍተኛ የጸጥታ አካላትና የሁለቱ ዞኖች ዋና አስተዳዳሪዎች በአዋሳኝ አካባቢዎች ያለውን ሰላም በዘላቂነት ለመጠበቅ ውይይት አካሂደዋል።

የመተከል ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አትንኩት ሹቱ፤የህግ የበላይነትን ለማስከበርና የህብረተሰቡን ደህንነት ለመጠበቅ የሁለቱ የጸጥታ አካላት እና አመራሩ ከመቼውም በላይ በጋራ መስራት እንደሚገባ ገልጸዋል።

በቀጠናው የሚስተዋለውን ችግር ለማስወገድ የሚወሰዱ እርምጃዎችን በጋራ በመወሰን የህብረተሰቡን ወጥቶ የመግባት መብት ማስጠበቅ እንደሚገባም ገልጸዋል።

የመተከል ዞን ኮማንድ ፖስት ሰብሳቢ ኮሎኔል መንገሻ ታከለ፣የጦር መሳሪያ ዝውውር፣የተለያዩ የስርቆት ወንጀሎች፣የሰዎች እገታና ግድያ፣የመሬት ወረራና ሌሎች የህብረተሰቡን አብሮነት የሚለያዩ የጽንፈኝነት አጀንዳ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ሃይሎችን በጋራ ለማስወገድ የጋራ ጥምር ኮሚቴው በትኩረት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።

በየደረጃው ያለው የጸጥታ አካል ሰላምና ጸጥታን ለማስፈን ከህብረተሰቡ ጋር በቅንጅት መስራት እንዳበት የገለጹት መኮንኑ የሀገርንና የህዝብን ሰላም የሚነሱ ሃይሎችን በማስወገድ ረገድ በጥብቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የሁለቱ ዞን አዋሳኝ አካባቢ ህዝቦች ለዘመናት የጋራ እሴት ገንብተው የሚኖሩ መሆናቸውን ገልጸው ይህ አንድነትና አብሮነት የማይመቻቸው አካላት የሚፈጥሩትን ግጭት በዘላቂነት ማስወገድ የሚቻለው በጋራ በመቆም እንደሆነ የተናገሩት ደግሞ የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ቴዎድሮስ እንዳለ ናቸው።

ግብረ ሃይሉ ለሰላም እጦት መንስኤ ናቸው ያላቸውን አጀንዳዎች በመለየት እና በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በመምከር የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ውይይቱ ተጠናቋል።

በውይይት መድረኩ የሀገር መከላከያ ሰራዊት እና የፌድራል ፖሊስ ከፍተኛ መኮንኖች፣የሁለቱ ዞኖችና ከፍተኛ የዞንና የወረዳ አመራሮችና የጸጥታ አካላት ተገኝተዋል።

Amhara Police Commission

13 Oct, 10:28


ከቆላድባ ከተማ ወጣቶች ጋር በወቅታዊ የሰላምና የልማት ስራዎች ጋር ተያይዞ ውይይት ተደረገ።

ከቆላድባ ከተማ ወጣቶች ጋር በወቅታዊ የሰላምና የልማት ስራዎች ጋር ተያይዞ የዞን አመራሮች በተገኙበት ውይይት ተደርጓል።

የከተማዋን ዘላቂ ሰላም በማፅናትና ልማትን በማረጋገጥ በኩል ወጣቶች የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ የተገለፀ ሲሆን የከተማውን ሰላም ለማረጋገጥ የሰላም ካውንስል ተቋቁሟል ሲል የወረዳውን ኮሙዩኒኬሽን ጠቅሶ የማዕከላዊው ጎንደር ዞን ኮሚኒኬሽን ነው።

Amhara Police Commission

12 Oct, 12:41


ከመጀመሪያ ባሏ የጸነስችውን ልጅ ሁለተኛ ባሏ እንዳያውቅ የ7ወር በላይ የሆነውን ፅንስ አቋርጣ ሽንት ቤት የከተተችው ተጠርጣሪ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች።

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር በንጉስ ተክለሀይማኖት ክፍለከተማ ቀበሌ 03 ልዩ ቦታው ቦሌ ኮንደምንዬም አካባቢ ከሁለተኛ ባሏ ጋር የፋሲካ በዓል እንደተዋወቁ እና በተከራዬው ቤት አብረው መኖር ይጀምራሉ ።
ከዛም ሰውነቷ እና ሆዷ እየጨመረ ሲመጣ ይሄነገር ምንድነው ሲል ባል ይጠይቃል ? እርግዝና እንዳልሆነ እና ቦርጭ መሆኑን ፍጹም እንዳይጠራጠር ታሳምነዋለች።

ፅንሱ ቀኑ እየጨመረ ሲመጣ ለባሏ እንደአመማት እና ወደግል ስረዋ እንደማትሄድ ትነግረዋለች ባሏም ይሄን ተቀብሎ በጠዋቱ ወደስራው ይሄዳል።ከላይ በተጠቀሰው ቀን ከጠዋቱ 1:30 በሚሆንበት ግዜ አከራዮች እና ሌሎች ተከራዮች አለመኖራቸውን አረጋግጣ ጽንሱ የሚቋረጥበትን መንገድ ምቹ ሁኔታ ፈጥራ ጽንሱን አቋርጣ ሽንት ቤት መጣሏ ለፖሊስ መረጃ ይደርሳል ።

ፖሊስ የደረሰውን መረጃ መሠረት አድርጎ ተጠርጣሪዋን ከእነ ባሏ በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን ያከናውናል ።ተጠርጣሪዋ ከዚህ በፊት ባህርዳር ከነበረው ባሏ አርግዛ እንደነበር እና አሁን የአገባችው ባሏ ቅርብ ግዜ መሆኑን ፖሊስ ከተጠርጣሪዋ እና ከተለያዩ አካላት ያሰባሰበው ማስረጃ መሠረት አድርጎ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ተጨማሪ የህክምና እና ሌሎች ማስረጃዎችን በማሰባሰብ ላይ መሆኑን የ4ኛ ፖሊስ ጣቢያ የታክቲክ ወንጀል ምርመራ ሀላፊ ምክትል ኢንስፔክተር አንዳርግ ደግዋለ ገልጸዋል።

የክፍል ሀላፊው አያይዘው እንደገለጹት ህብረተሰቡ የተፈጸመውን ድርጊት በማውገዝ ተጠርጣሪዋን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከመጀመሪያ ጥቆማ ከመስጠት ጀምሮ ሌሎች ማስረጃዎችን ለፖሊስ እስከ መስጠት ድረስ ለአከናወኑት ተግባር ከፍተኛ ምስጋና አቅርበው በቀጣይ እንዲህ አይነት ወንጀሎች እንዳይስፋፉ ከፖሊስ ጋር ያለውን ቅንጅታዊ አሰራር አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

መረጃው፦የደብረማርቆስ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ ነው።

Amhara Police Commission

12 Oct, 09:11


በደሴ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ተቋማት የ2017 ዓ/ም የሶስት ወር የስራ አፈፃፀም ውይይት ተካሄደ።

በደሴ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ መምሪያ አማካኝነት በከተማዋ የሚገኙ የዋና ፖሊስ ጣቢያ አመራሮች የክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሃላፊዎች እና የሚሊሻ ፅ/ቤት አመራሮች በተገኙበት ግምገማው የተካሄደ ሲሆን የአምስቱም ዋና ፖሊስ ጣቢያዎች የክፍለ ከተማ ፀጥታ ቢሮዎች በሶስት ወር ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።

የፖሊስ መምሪያ ሃላፊው ኮማንደር አበባው አሻግሬ የደሴ ከተማን ሰላም ለማስጠበቅ በሶስት ወር ውስጥ የተሰሩ ውጤታማ ስራዎች ሊጠናከሩ ይገባል ብለዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ሰላም እና ፀጥታ መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር ሰይድ አሊ በግምገማው ማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡ ሲሆ ስራዎችን በጠንካራ ቅንጅት መስራት መቻላችን ከተማችን ሰላም ሁና እንድትቀጥል ሆኗል ብለዋል።

ግምገማው ላይ የተገኙ አመራሮች በቀረበው ሪፖርት ላይ ሀሳብ አስተያየት ሰጥተው ግምገማው ተጠናቋል ።

ዘገባው የደሴ ከተማ አስተዳደር ህዝብ ግንኙነት

Amhara Police Commission

10 Oct, 08:13


በታች አርማጭሆ ወረዳ ያለውን አንፃራዊ ሰላም ይበልጥ በማሳደግና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ

በመድረኩ በወረዳው ከሙሴ ባንብ ከተማ እና አካባቢው የተወጣጡ የህብረተሰብ ክፍሎች የተገኙ ሲሆን በወረዳው ያለውን አንፃራዊ ሰላም ይበልጥ በማሳደግና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

እየተካሄደ ባለው የሰላም መድረክም አሁን ያለውን አንፃራዊ ሰላም ይበልጥ በማሳደግና ዘላቂ ሰላም እንዲረጋገጥ በማድረግ በኩል ሁሉም ባለድርሻ አካል ሃላፊነቱን በአግባቡ ሊወጣ እንደሚገባ ተሳታፊዎች ገልፀዋል።

በመሆኑም "ሰላም" ለዘላቂ ልማት ያለው ፋይዳ ትልቅ በመሆኑ ህብረተሰቡ ከመንግስት ጎን ሁኖ ተሰልፎ የአካባቢውን ሰላም ሊያረጋግጥ እንደሚገባ ተገልጿል።

መንግስትም የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ነው በምክክር መድረኩ የተገለፀው።

ምንጭ፥ማዕከላዊ ጎንደር ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን።