****
የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ከስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፣ ከአፖስቶ ካምፓስ እና ከመሠረታዊ ፖሊስ ስልጠና አካዳሚ ለተዉጣጡ ለሰዉ ሀብት ስራ አመራር መምሪያ ሰራተኞች እንዲሁም ለሴት የፖሊስ አመራር እና አባላት ስልጠና ተሰጥቷል ።
በስልጠና ማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ በመገኘት የስራ መመሪያ የሰጡት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ የአስተዳደር ልማት ም/ፕረዝዳንት ም/ኮሚሽነር ጌቱ ተ/ዮሐንስ በዩኒቨርሲቲው ለሰው ሀብት ስራ አመራር ስር ለሚሰሩ አመራርና ሰራተኞች የተሰጠው ስልጠና መሰረታዊ የሆነና ሁሉም ሰዉ አዉቆ እንደ መርህ ይዞ ሊተገብረዉ የሚገባ ስልጠና እንደሆነ ተናግረዋል ።
የሁለቱም ስልጠናዎች አላማ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች አመራርነት ሚና የስራ ብቃት የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችል ግንዛቤ መፍጠር እና የሰዉ ሀብት አስተዳደር አመራሮችና ባለሞያዎች የሰዉ ሀብት ስራ በአግባቡ በማወቅ በስራ አፈጻጸም ሂደት የሚታዩ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ለማድረግ አቅም የሚፈጥር ፣ ዉሳኔ የመስጠት እና ችግሮችን የመፍታት ብቃት ለማጎልበት ተስቦ የተሰጠ ስልጠና እንደሆነ በቀረበዉ ሪፖርት ተጠቁሟል ።