Ethiopian Police University Official Page @epupage Channel on Telegram

Ethiopian Police University Official Page

@epupage


Protect with courage ;Serve with Compassion!
EPU Social Media link
@https://www.facebook.com/ethiopianpolice

Ethiopian Police University Official Page (English)

Welcome to the Ethiopian Police University Official Page, also known as @epupage on Telegram! This channel serves as the official platform for the Ethiopian Police University, where individuals can stay updated on news, events, and announcements related to the university. Founded with the mission to protect with courage and serve with compassion, the Ethiopian Police University is committed to providing high-quality education and training to future law enforcement professionals. Whether you are a current student, alumni, or simply interested in the field of policing, this channel is the perfect place to connect with like-minded individuals and stay informed on the latest developments within the university. Join us on this exciting journey of learning, growth, and service. For more updates, you can also follow our social media links on Facebook at @https://www.facebook.com/ethiopianpolice. We look forward to having you as part of our community at the Ethiopian Police University Official Page!

Ethiopian Police University Official Page

13 Feb, 13:51


የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ለሰዉ ሀብት ስራ አመራር እና ለሴት የፖሊስ አመራር እና አባላት ስልጠና ሰጠ
****
የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ከስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፣ ከአፖስቶ ካምፓስ እና ከመሠረታዊ ፖሊስ ስልጠና አካዳሚ ለተዉጣጡ ለሰዉ ሀብት ስራ አመራር መምሪያ ሰራተኞች እንዲሁም ለሴት የፖሊስ አመራር እና አባላት ስልጠና ተሰጥቷል ።
በስልጠና ማጠቃለያ መርሐ ግብሩ ላይ በመገኘት የስራ መመሪያ የሰጡት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ የአስተዳደር ልማት ም/ፕረዝዳንት ም/ኮሚሽነር ጌቱ ተ/ዮሐንስ በዩኒቨርሲቲው ለሰው ሀብት ስራ አመራር ስር ለሚሰሩ አመራርና ሰራተኞች የተሰጠው ስልጠና መሰረታዊ የሆነና ሁሉም ሰዉ አዉቆ እንደ መርህ ይዞ ሊተገብረዉ የሚገባ ስልጠና እንደሆነ ተናግረዋል ።
የሁለቱም ስልጠናዎች አላማ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች አመራርነት ሚና የስራ ብቃት የበለጠ ለማጠናከር የሚያስችል ግንዛቤ መፍጠር እና የሰዉ ሀብት አስተዳደር አመራሮችና ባለሞያዎች የሰዉ ሀብት ስራ በአግባቡ በማወቅ በስራ አፈጻጸም ሂደት የሚታዩ ክፍተቶች እንዲስተካከሉ ለማድረግ አቅም የሚፈጥር ፣ ዉሳኔ የመስጠት እና ችግሮችን የመፍታት ብቃት ለማጎልበት ተስቦ የተሰጠ ስልጠና እንደሆነ በቀረበዉ ሪፖርት ተጠቁሟል ።

Ethiopian Police University Official Page

10 Feb, 07:58


ለአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አመራሮች ስልጠና እየተሰጠ ነው
**
ካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከውጭና ከሀገር ውስጥ የተለያዩ ተቋማት ጋር በትምህርትና ስልጠና ፣ በምርምር እንዲሁም በማህበረሰብ አገልግሎት በጋራ እና በትብብር የሚሰራበትን አድማስ በማስፋት ከመደበኛው የትምህርትና ስልጠና ባሻገር የተለያዩ ተቋማት ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ የሚያስችል ስልጠና በየጊዜው እየሰጠ ይገኛል፡፡
ዩኒቨርሲቲው ይህንኑ ተግባር አጠናክሮ በማስቀጠል ከአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ጋር በጋራ ለመስራት ባደረገው የጋራ የመግባቢያ ሰነድ መሰረት የኮሚሽኑን አመራርና ባለሙያዎች በዛሬው ዕለት ስልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ስልጠናውን ያስጀመሩት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ በባህሪው ከፖሊስ የስራ ባህሪ ተልዕኮ ጋር የሚገናኝ እና ተቀራራቢ በመሆኑ ህይዎታቸውን ለአደጋ አጋልጠው የሌሎችን ህይዎትና ንብረት ከአደጋ ለማዳን ለሚያደርጉት ታላቅ ስራ ተገቢውን የሙያ ተልዕኮ አፈጻጸም እንዲኖራቸው ለማስቻል ስልጠናው ጉልህ ሚና እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡
ሙያው በባህሪው ራስን መስጠት እና ጽናትን የሚጠይቅ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ ስልጠናው የተሻለ ፈጻሚ እና የተልዕኮ አወጣጥ ስርዓትን በማሻሻል ሰልጣኞች ከስልጠናው ህዝብ በአገልግሎቱ እንዲረካ የሚያደርግ ግብዓት እንደሚያገኙ አስገንዝበዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

08 Feb, 12:58


በተባበሩት ዐረብ ኢምሬት የዱባይ ፖሊስ ልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት አደረጉ
*********
የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፣ሰንዳፋ
በተባበሩት ዐረብ ኢምሬት የዱባይ ፖሊስ ልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ጉብኝት አድርገዋል።
የልዑካን ቡድን አባላቱ ጉብኝት ባደረጉበት ወቅት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከምርምር ፣ማማከርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ ጋር በዩኒቨርሲቲው የተለያዩ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉ ስልጠናዎችን ለመስጠት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
በውይይታቸው በተለይም የሰው አልባ አውሮፕላን ወይም ድሮን (Unmanned Aerial Vehicle)፣ ስልጠናን ለመስጠት ያሉ አስቻይ ሁኔታዎች ላይ የመከሩ ሲሆን በመጨረሻም የፎረንሲክ ምርመራ እና የምርምር የልህቀት ማዕከልን ጎብኝተዋል።

Ethiopian Police University Official Page

07 Feb, 13:55


የኢትዮጵያ ፖሊሲ ዩኒቨርሲቲ ከውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ጋር አብሮ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ
**
ጥር /30 /2017ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በጥናትና ምርምር ከተለያዩ ተቋማቶች ጋር አብሮ በምስራት ላይ ይገኛል በዛሬው ዕለትም ከውጪ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ጋር አብሮ መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ የሁለቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ውይይት አካሂደዋል።
በውይይቱ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የጥናትና ምርምር ማማከር ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ እንደገለጹት ቀጠናዊና አለም አቀፍ የሆኑ ሠላምና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሁለቱ ተቋማቶች አብሮ መስራት አስፈላጊና ውጤታማ እንደሚያደርግ ገልጸዋል። አክለውም ድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች፡- ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር፣ ሽብርተኝነት ፣የአደንዛዥ እፅ ዝውውር እና ሌሎች የአለም አቀፍ ወንጀሎችን ለመከላከል የሚያስችል ጥናትና ምርምር አብሮ ማካሄድ እንደሚቻል ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት የዋና ዳይሬክተር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ተስፋዬ በዛብህ (ዶ/ር) እንደገለጹት የሁለቱም ተቋማት ኃላፊነት የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ማስከበር መሆኑን ተናግረው ይህንኑ ጉዳይ ተቋማት በጋራ በመተባበር በጥናትና ምርምር የተደገፈ ስራዎችን መስራት እንደሚቻል ገልፀዋል።
በመጨረሻም የሁለቱን ተቋማት ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር በቀጣይ ቴክኒካል ኮሚቴዎች በመዋቅር ግንኙነቱን ወደ ላቀ ደረጃ ማድረስ እንደሚገባ በውይይቱ ተመላክቷል።

Ethiopian Police University Official Page

05 Feb, 06:34


https://www.facebook.com/100077758515468/posts/pfbid0j5UkDQNvB7H6R5S4XYE65s9YcsVXNDUdLCCveLhJJ3vbgGcKEvk4BERfEiMiRZZYl/

Ethiopian Police University Official Page

04 Feb, 16:03


ለአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለምልምል የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል ውይይት ተካሄደ
***
ጥር 27/2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ለሁለት ሺህ (2000) ደንብ አስከባሪ ኦፊሰሮች ስልጠና ለመስጠት የሚያስችል የቅድመ ዝግጅት ውይይት በሻአለቃ ዘሪሁን ተፈራ ከተመራው ልዑክ ቡድን ጋር በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ውይይት ተካሂዷል፡፡
በውይይቱ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ለአባላቱ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ፖሊስ ዩኒቨርሲቲው ከአዲስ አበባ ከተማ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን ጋር አብሮ የመስራት ልምድን ከበፊቱ ይበልጥ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል ። አያይዘውም የደንብ ማስከበር ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው ደንብ ተላላፊዎችን ከስህተት ማረም የሚችሉበትን በቂ ዕውቀት ያገኛሉ ብለዋል፡፡ በመጨረሻም በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራር ስልጠና ዋና ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዋ/ኢ/ር ጉግሳ ገ/ስላሴ ስለ ስልጠናው ሂደት እና አፈፃፀም በውይይቱ ላይ ለተሳተፊ የልዑክ አባላት ገለፃ አድርገዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

03 Feb, 23:50


በጅግጅጋ ማሰልጠኛ ለሚገኙ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ መሰረታዊ የፖሊስ ሰልጣኞች የፖሊሳዊ ስብዕና ግንባታ እና የመዝናኛ ፕሮግራም ተካሔደ
*****
ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በጅግጅጋ ማሰልጠኛ ለሚያሰለጥናቸው የ25ኛ ዙር መሰረታዊ የፖሊስ ሰልጣኞች የፖሊሳዊ ስብዕና ግንባታ እና የመዝናኛ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት ተካሔዷል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ በሚገኘው ዋናው ካምፖስ በተለያዩ የትምህርት መርሐ-ግብሮች በመደበኛው የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራሞች ከሀገራችን አልፎ ለጎረቤት ሀገራት ጭምር የውጭ የትምህርት ዕድል በመስጠት ለፖሊስ የሙያ ዘርፍ የላቀ ደረጃ መድረስ የበኩሉን አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው የሀገራችንን የፖሊስ የሙያ ዘርፍ የበለጠ ለማዘመን በሰው ሀይል ፣ በእውቀት፣ ክህሎትና አመለካከት የበለጸገ ይሆን ዘንድ በትኩረት እየሰራ ሲሆን በጅግጅጋ ማሰልጠኛ በስልጠና ላይ ለሚገኙ የ25ኛ ዙር መሰረታ የፖሊስ ሰልጣኞ በፌደራል ፖሊስ የኪነጥበባት ስራዎች የስራ ክፍል ጋር በመተባበር የኦኬስትራ እና ቲያትር ሙያተኞች በቦታው ተገኝተው የፖሊሳዊ ስብዕና ግንባታ እና የመዝናኛ ፕሮግራም ለሰልጣኞች አቅርበዋል።

Ethiopian Police University Official Page

03 Feb, 11:45


ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ ፖሊስ የኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከኦሮሚያ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ጋር በመተባበር የሙያ ብቃት ምዘና ፈተና (COC) ለመስጠት ስምምነት ላይ ደርሶ አብሮ በመስራት ላይ ይገኛል ። ስለሆነም በነርሲነገ ደረጃ አራት፡ በህክምና ላቦራቶሪ ደረጃ አራት እና በፋርማሲ ደረጃ አራት የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ለመውሰድ የምትፈልጉ ተመዛኞች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳስባለን።
ተመዛኞች ማሟላት የሚገባቸው ቅድመ ሁኔታዎች የሚከተሉ ናቸው
1. በተጠቀሱት ሙያዎች በደረጃ አራት መመረቃቸውን የሚያሳይ የትምህርት ማስረጃ( የምስክር ወረቀትና የውጤት ዝርዝር/student copy)

2. የስምንተኛ ክፍልና 10ኛክፍል ክልላዊና ብሔራዊ ፈተና ውጤት ካርድ

3. ለምዘናው የሚያስፈልገውን ክፍያ (ለነርሲንግና ለፋርማሲ ብር 963 ለህክምና ላቦራቶሪ ብር 1027)

4. አራት 3በ4 ጉርድ ፎቶግራፎችን

በመያዝ እስከ የካቲት 03 /2017 ዓ/ም ሰንዳፋ በሚገኘው የኢት/ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በስራ ሰዓት በአካል በመቅረብ መመዝገብ ይኖርባቸዋል።
ማሳሰብያ
በአካል መመዝገብ ለማትችሉ ከዚህ በታች በተቀመጠው ሊንክ በመጠቀም መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን
https://docs.google.com/spreadsheets/d/1cBMpGcuN2zJtau_TbbpPUCDpyiCKWMeM6OdySv0EdMY/edit?usp=sharing
ለበለጠ መረጃ +251902765295 ላይ ይደውሉ!

Ethiopian Police University Official Page

01 Feb, 19:37


ለ25ኛ ዙር ምልምል የፖሊስ ሰልጣኞች የፖሊሳዊ ስብዕና ግንባታ እና የመዝናኛ ፕሮግራም ተካሔደ
*
ጥር
24 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በአዋሽ 7 ማሰልጠኛ የመሰረታዊ ፖሊስ ስልጠና አካዳሚ ለሚያሰለጥናቸው የ25ኛ ዙር ምልምል የፌደራል ፖሊስ ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት የፖሊሳዊ ስብዕና ግንባታ እና የመዝናኛ ፕሮግራም ተካሔዷል።
ፕሮግራሙን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የውጭና ህዝብግንኙነት ዋና ክፍል ከስልጠና ም/ፕሬዝዳንት እና በፌደራል ፖሊስ የኪነጥበባት ስራዎች ዋና ክፍል ጋር በጋራ በመሆን አዘጋጅተውታል።

Ethiopian Police University Official Page

01 Feb, 14:10


https://www.facebook.com/100077758515468/posts/635553472379931/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Ethiopian Police University Official Page

30 Jan, 18:10


https://www.facebook.com/100077758515468/posts/634286809173264/?mibextid=rS40aB7S9Ucbxw6v

Ethiopian Police University Official Page

29 Jan, 20:04


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ግምገማ ተካሔደ
***
ጥር 21/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከመደበኛው ዕቅድና ደራሽ ስራዎች ባሻገር የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ዕቅድን መሰረት በማድረግ ታቅደው በተከናዎኑ ተግባራት እና ያስገኙት ውጤት እንዲሁም በቀጣይ ግዜያት ውስጥ መሰራት ስለሚገባቸው ጉዳዮች ላይ ግምገማ ተካሂዷል፡፡
በግምገማ መርሐግብር ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ጀኔራል መስፍን አበበ ታቅደዉ የተሳኩ ተግባራትን ለወደፊት የበለጠ መስራት እና የታዩ ክፍተቶችን ደግሞ ትኩረት በመስጠት በጋራ መንግስታዊ እና ተቋማዊ ለዉጥ በተለይ ዲጅታል ኢትዮጵያን ለመፍጠር በቀጣይ ጊዜ በትምህርትና ስልጠና፣ በአስተዳደር እና በምርምር በተሻለ ፍጥነትና ጥራት ማከናወን እንደሚገባ ተናግረዋል ።
በግምገማውም በዩኒቨርሲቲው ስር የሚገኙ የአራቱ ምክትል ፕሬዝዳንቶች እና የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት መምሪያ የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ በእያንዳንዱ ም/ፕሬዝዳንቶች ያሉ ጠንካራ እና ደካማ ጎኖችን በመለየት ክፍተቶችን ሞልቶ ጠንካራ የትምህርትና ስልጠና ተቋም በመፍጠር እና ዘመኑን የዋጀ ቴክኖሎጅን በመጠቅም እንዲሁም ፖሊሳዊ ዲስፕሊን በማጠናከር የፖሊስ አገልገሎትን በጥራት ለመስጠት በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

26 Jan, 21:55


https://www.facebook.com/100077758515468/posts/pfbid02C8H2yuUE8LDw4iv7TcdZL9DrKNmsFbdV9LqUVwDp6kEHAKDX8ASLqixkRPMyK7rJl/

Ethiopian Police University Official Page

25 Jan, 16:17


የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በስድስተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን የከፍተኛ ማዕረግ መኮንኖች አስመረቀ
***
ጥር 17/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ከፌደራል ፖሊስ ፣ ከሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ፣ ከተለያዩ የክልል ፖሊስ ኮሚሽኖች ተውጣጥተው ስልጠና የወሰዱ 307 ከኢንስፔክተር ወደ ዋና ኢንስፔክተር ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ የከፍተኛ ማዕረግ የፖሊስ መኮንኖች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አዋሽ 7 የአመራርና አቅም ግንባታ ስልጠና ማዕከል በዛሬው ዕለት በድምቀት ተመርቀዋል።
በምርቃት ፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ገሚካኤል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ባለፋት ስድስት ዓመታት የሪፎርም ስራዎችን በብቃት የሰራ በከፍተኛ ደረጃ እያደገና እየዘመነ የመጣ ተቋም ሆኗል በፌዴራል ፖሊስ ብቻ የቆመ ሳይሆን አጠቃላይ የአገራችንን ፖሊስ ለማዘመንና በተቻለ መጠን ስታንዳርዱን በጠበቀ መልኩ እንዲያድግ ለማድረግ እንደ ኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
ለረጅም ጊዜ በኮሌጅነት ያገለግል የነበረው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ወደ ሙሉ ዩኒቨርሲቲነት ከተሸጋገረ በኋላ ተበታትነው ይሰጡ የነበሩ የፖሊስ ትምህርትና ስልጠናን በአንድ ማዕከል እንዲመራ በማድረግ በዚህ ውስጥ ደግሞ በተለይ የእኛ ስብራት የነበረውን የማዕረግ አሰጣጥ ስነ ስርዓትን ሁሉም በየደረጃው የሚገኝ አባል የደረሰበትን የማዕረግ እርከን የሚመጥነውን ስልጠና እንዲያገኝ በማድረግ ዩኒቨርስቲው ከፍተኛውን ድርሻው እየተወጣ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

Ethiopian Police University Official Page

25 Jan, 02:39


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በአካል እጀባ እና በአድማ መቆጣጠር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ
***
ጥር 16/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ሰንዳፋ
ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ከወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ለተወጣጡ የፖሊስ አመራሮችና አባላት ለከፍተኛ ባለስልጣናት አጠባበቅ የአካል እጀባ እና የአድማ መቆጣጠር በሁለተኛ ዙር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ ።
በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ የምርምር፣ ማማከርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሀኑ ስልጠናው አለም አቀፍ ልምድና ተሞክሮ ባለቸዉ ባለሙያዎች መሰጠቱ ጥሩ አጋጣሚ መሆኑን ተናግረዉ በስልጠና ያገኙትን እዉቀት እና ክህሎት ህዝባዊ አመለካከት በመጠቀም ቀደም ሲል ከሚያውቁት ጋር በማቀናጀት የበለጠ ዉጤታማ የሆነ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አሳስበዋል ።
በሌላ በኩል ስልጠናዉን አስመልክቶ ሪፖርት ያቀረቡት ኢ/ር ዋቅቷላ ታመነ ስልጠናዉ መሰረታዊ የአድማ መቆጣጠር እና መሰረታዊ የከፍተኛ ባለስልጣናት ጥበቃ እና እጀባ ስልጠናን በንድፈ ሀሳብ እና በተግባር ከዱባይ በመጡ አሰልጣኞች በስፋት መሰጠቱን ተናግረዋል።

Ethiopian Police University Official Page

23 Jan, 23:58


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለሚገኘው የቋንቋ ላብራቶሪ ከፈረንሳይ ኢምባሲ የቁሳቁስ ድጋፍ ተደረገለት
*
ጥር 15/05/2017 ዓ/ም የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፈረንሳይ ኢምባሲ ጋር ባደረገው ስምምነት እንዲሁም ባለው በጋራና በትብብር የመስራት ልምድ መሠረት በዩኒቨርሲቲ ለሚገኘው የቋንቋ ላብራቶሪ ከፈረንሳይ ኢምባሲ የቁሳቁስ ድጋፍ ተደርጎለታል።
ለቋንቋ ላብራቶሪው ኮሎኒል ሰባስቲያን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ሚሊታሪ አታሺ እና ሜጄር አርኖልድ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኢምባሲ የፕሮጀክት ማናጀር አማካኝነት ለዩኒቨርስቲው አመራሮችና አባላት የፈረንሳኛ ቋንቋ ላቭራቶሪ ማስተማሪያነት የሚያግዝ ዲስክቶፕ ኮምፒዩተር እና የጆሮ ማዳመጫዎችን ነው ድጋፍ ያደረጉት። ኮሎኒል ሰባስቲያን በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ሚሊታሪ አታሺ እና ሜጄር አርኖልድ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ ኢምባሲ የፕሮጀክት ማናጀር ለወደፊቱ የቋንቋ ላቭራቶሪውን ለማሳደግ የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርጉ ተናግረዋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ም/ኮምሽነር ጀነራል እና የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት መስፍን አበበ እንደተናገሩት ለወደፊቱ ከዩኒቨርሲቲው አመራሮችና አባላት በተጨማሪ የግቢ ተማሪዎችን ያሳተፈ በትርፍ ጊዜያቸው ይህን ቋንቋ መማር የሚችሉበትን ዕድል ማመቻቸት እንደሚገባ አሳስበዋል።

Ethiopian Police University Official Page

23 Jan, 16:56


ለሰዉ ሀብት ስራ አመራር እና ለሴት የፖሊስ አመራር እና አባላት ስልጠና እየተሰጠ ነዉ
******
ጥር 15/2017ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ ከስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ዩኒቨርሲቲው ፣ ከአፖስቶ ካምፓስ እና ከመሠረታዊ ፖሊስ ስልጠና አካዳሚ ለተዉጣጡ የሰዉ ሀብት ስራ አመራሮችና እና ለሴት የፖሊስ አመራር እና አባላት ስልጠና እየተሰጠ ነዉ።
በስልጠና ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርስቲ የሰዉ ሀብት ስራ አመራር መምሪያ ኃላፊ አቶ አደነ አስረስ በንግግራቸው ስልጠናዉ ትልቅ ጥቅም የሚያስገኝ እና የመምራት አቅምንና እዉቀትን የሚያሳድግ በመሆኑ ስልጠናውን በአግባቡና በጥሩ ስነምግባር መከታተል አንደሚገባ ለሰልጣኞች አሳስበዋል።
ስልጠናው ለተከታታይ አስራ አራት (14) ቀናት የሚሰጥ ሲሆን በስልጠናው ላይ የስኬት እቅድ እና አመራር ፣
የሰዉ ሀይል አስተዳደር ፣የብቃት ማዕቀፍ እና የሙያ መሪ የስልጠና አስተዳደር ላይ ያተኮረ ስልጠና እንደሚሰጥ ተገልጿል ።
በተጨማሪም ለሴት የፖሊስ አመራር እና አባላት ለተከታታይ ዘጠኝ (9)ቀናት የሴቶች የስራ አፈፃፀም እና አመራር ፣ የሴቶች አመራር እና ፈጠራ እንዲሁም የስርዓተ ፆታ ልማት እና አስተዳደር ላይ ያተኮረ ስልጠና ይወስዳሉ።

Ethiopian Police University Official Page

20 Jan, 23:07


የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የእጅ ኳስ ፕሮጀክት ዋንጫና የምስክር ወረቀት ተረከ
**
*
ጥር 12/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኦሮሚያ ክልል ባቱ ከተማ በተካሔደው ክልላዊ የወጣቶች ስፖርት ውድድር የተሳተፈው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከ17 ዓመት በታች የእጅ ኳስ ፕሮጀክት ቡድን ተጋጣሚውን አምቦ ከተማን በሰፊ የነጥብ ልዩነት ማሸነፋን ተከትሎ የወርቅ ሜዳሊያ እና የምስክር ወረቀት ተረክቧል።
ለእጅ ኳስ ፕሮጀክት ቡድኑ ጨዋታውን አሸንፎ ዋንጫውን ይዞ ሲገባ በዩኒቨርሲቲው አቀባበል ተደርጎለታል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የእጅ ኳስ ፕሮጀክት በ2016 ዓ.ም በተካሔደው የመላው ኦሮሚያ ዓመታዊ የስፖርት ውድድር በተሳተፈባቸው የእጅ ኳስ ውድድሮች አሸነፊ በመሆን ለዋንጫ የበቃ መሆኑ ይታወቃል።

Ethiopian Police University Official Page

18 Jan, 17:19


የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከ17 ዓመት በታች በተደረገ የእጅ ኳስ ጨዋታ አሸነፈ
***********
ጥር 10/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኦሮሚያ ክልል እየተካሔደ ባለው ክልላዊ የስፖርት ውድድር የተሳተፈው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከ17 ዓመት በታች የእጅ ኳስ ፕሮጀክት ቡድን ተጋጣሚውን አምቦ ከተማን በሰፊ የነጥብ ልዩነት በማሸነፍ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት መሆን ችሏል።

Ethiopian Police University Official Page

17 Jan, 03:28


https://www.facebook.com/100077758515468/posts/pfbid0oNMjkQRmwVRddvNJYL355MEYGXVEczDRh1ZZxTDPwrxY9t7xsW1pnBgMSwTcvKfxl/?app=fbl

Ethiopian Police University Official Page

12 Jan, 15:26


116ኛው ሀገር አቀፍ የኢትዮጵያ ፖሊስ ቀን በዓልን ምክንያት በማድረግ ሲካሄድ የነበረው ውድድር ተጠናቀቀ
********
ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ
በ2017 ዓ.ም የሚከበረውን 116ኛ ብሔራዊ የፖሊስ ቀንን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሚገኙ የሥራ ክፍሎች መካከል ሲካሔድ የነበረው ስፖርታዊ ውድድር በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
ከታኅሣሥ 22 ቀን ጀምሮ እስከ ጥር 4 ቀን 2017 ዓ.ም በተደረጉ ስፖርታዊ ውድድሮች የወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ ከፍተኛ ዋንጫ በመሰብሰብ 1ኛ ደረጃ በመሆን አጠናቋል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተሳተፈባቸው እያንዳንዱ ስፖርታዊ ውድድሮች ሜዳልያ እና ዋንጫዎችን ያገኘ ሲሆን በወንዶች የገመድ ጉተታ ውድድር በአስደናቂ ሁኔታ ከፌደራል ፖሊስ ሁሉም ጠቅላይ መምሪያዎች 1ኛ በመውጣት በበላይነት አጠናቋል።

Ethiopian Police University Official Page

11 Jan, 00:37


በአፖስቶ ካምፓስ በስልጠና ላይ የሚገኙ መደበኛ ሰርተፊኬት ዕጩ መኮንኖች ለአቅመ ደካማ የማህበረሰብ ክፍሎች ማዕድ አጋሩ
**
ጥር/2/2017 ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፓስ በስልጠና ላይ የሚገኙ የ25ኛ ዙር መደበኛ ሰርተፊኬት ዕጩ መኮንኖች የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ በአካባቢው ለሚገኙ አቅመ ደካማ የማህበረሰብ ክፍሎች ማዕድ አጋርተዋል።
ዕጩ መኮንኖቹ ከ40 ሺህ ብር በላይ ከደመወዛቸው በማዋጣት ለአቅመ ደካማ የማህበረሰብ ክፍሎች ለበዓል የሚሆን የዶሮና እንቁላል መግዣ ብር፣ ዱቄት፣ ዘይትና ሽንኩርት ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በተመሳሳይ ካምፓሱም የፍራሽና ብርድ ልብስ ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል።
በዕለቱ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት በአፖስቶ ካምፓስ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ዋና ኢ/ር ዘሪሁን እንዳለ ይህ ተግባር የህዝብ ልጆችና አገልጋይ መሆናችሁን የሚያረጋግጥ ሲሆን የሀገርና የህዝብን ሰላም ከማስጠበቅ ሀላፊነታችሁ ባሻገር የማህበረሰቡ ማህበራዊ ህይዎት ለማሻሻል ያደረጋችሁት ድጋፍ የሚያስመሰግን ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በዕለቱ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የካምፓሱ ፖሊሳዊ አካል ብቃትና ስልቶች ክፍል አስተባባሪ ዋና ኢ/ር አስተያየት ጊታ ይህ መልካምነት ለራሳቸውም ሆነ ለስራቸው ጥሩ ስንቅ በመሆኑ በየትኛውም ቦታና ሁኔታ ውስጥ ሆነው በጎነታቸውን እንዲቀጥሉ አሳስበው ይህን ተግባር ላስተባበሩ ሁሉ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

Ethiopian Police University Official Page

10 Jan, 12:26


https://t.me/+NX2YJCVEXOtiNGE0
ማስታወቂያ
የኢትትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከመደበኛው መርሃ-ግብር በተጨማሪ በርቀት ትምህርት መርሃ-ግብር የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽ ለማድረግ በወንጀል መከላከል እና ፖሊስ ስራ አመራር የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት መስኮች የአንደኛ ዙር ትምህርት ለማስጀመር በደብዳቤ ቁጥር ኢፖዩ ትስ-13/129 ያለፉ ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ማሳወቃችን ይታወቃል፡፡ ስለሆነም ፈተና ወስዳችሁ ያለፋችሁ የፖሊስ አመራር እና አባላት ከዚህ በላይ በተዘጋጀው የምዝገባ ፎርም ላይ የተጠቀሰውን የቴሌግራም ሊንክ በመጠቀም እስከ ጥር 6/2017 ዓ/ም እንድትመዘገቡ እየገለፅን የቱቶሪያል ፕሮግራሙን በተመለከተ በቀጣይ የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

የርቀትና ተከታታይ ትምህርት ማዕከል

Ethiopian Police University Official Page

09 Jan, 17:37


በፖሊስ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ (TVET) የተከናወኑ ተግባራት፤ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ዉይይት ተካሔደ
**
ጥር/1/2017 ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፖሊስ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ (TVET) የተከናወኑ ተግባራት፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ላይ ከተለያዩ ተቋማት ጋር በመገናኘት በርካታ ተሞክሮዎችን በመቀመር በዛሬዉ ዕለት ዉይይት ተካሂዷል፡፡
በዉይይቱ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ም/ፕሪዝደንት ረ/ኮሚሽነር ደረጀ አስፋዉ የፖሊስ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ (TVET) ያለበትን ክፍተት ጥናትን መነሻ አድርጎ ለመፍታት የተሄደበት መንገድ የሚደነቅ መሆኑን ገልጸዉ ኮሌጁ(TVET) ያለበትን ችግር በመለየት እና ትኩረት በመስጠት ዘለቄታዊ መፍትሔ ማምጣት እንዳለበት ተናግረዋል ፡፡
በሌላ በኩል የፖሊስ ቴክኒክ እና ሙያ ኮሌጅ (TVET) የሚያስፈልጉ ግብዓቶች ቢሟሉ እንደ ዎርክ ሾፕ ማተሪያሪያል ፤ የተለያዩ አጋዥ መጽሀፍቶች፤ የመዋቅር አደረጃጀት እና የመሳሰሉ ችግሮች ቢቀረፉ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት እና ስልጠናዉ ስኬታማ ሊሆን እንደሚችል ተጠቁሟል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

04 Jan, 09:52


የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በእግር ኳስ ጨዋታ እና በገመድ ጉተታ አሸነፈ
********
ታህሳስ 26 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአስተዳደር ልማት ጠቅላይ መምሪያ ጋር ባደረገው የእግር ኳስ ጨዋታ 1ለ0 በሆነ ውጤት ያሸነፈ ሲሆን በተመሳሳይ ከአስተዳደር ልማት ጠቅላይ መምሪያ ጋር በወንዶች ገመድ ጉተታ ባደረገው ጨዋታ 2ለ0 አሸንፏል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም የሚከበረውን 116ኛ ብሔራዊ የፖሊስ ቀንን አስመልክቶ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በሚገኙ ጠቅላይ መምሪያዎች መካከል በተካሄደው ስፖርታዊ ጨዋታ በወንዶች ከፌደራል ፖሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ እና በሴቶች ከፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ ጋር ባደረገዉ የገመድ ጉተታ ጨዋታ በሁለቱም ጾታዎች በአስደናቂ ሁኔታ ማሸነፋ ይታወቃል።

Ethiopian Police University Official Page

03 Jan, 13:56


ለከፍተኛ ባለስልጣናት የአካል እጀባ የፖሊስ አመራርና አባላት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ
***
ታህሳስ 25/04 ቀን 2017ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለከፍተኛ ባለስልጣናት የአካል እጀባ (VIP) ጥበቃ የፖሊስ አባላትና አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው ዕለት ተጠናቋል፡፡
በስልጠና ማጠናቀቂያ ፕሮግራሙ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት ዋ/ኢ/ር ማርቆስ ግዛው መሰል ስልጠናዎች ከዚህ ቀደም በውጭ ሀገራት ሲሰጡ የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመው ስልጠናው በሀገር ውስጥ መሰጠቱ የሀገራችንን ልምድ ከማዳበራችንም ባሻገር ጥሩ ልምድና ወጭን ቀናሽ በመሆኑ በቀጣይም መሰል ስልጠናዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረው ሰልጣኞች የወሰዱትን ስልጠና ተግባር ላይ በማዋልና ለሌሎች በማስተማር ጭምር የተጣለባቸውን ከፍተኛ ሃላፊነት እንዲወጡ ተናግረዋል፡፡
ስልጠናውን በሚመለከት የስልጠና ሪፖርት ያቀረቡት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና አስተባባሪ የሆኑት ኢ/ር ዋቅቶላ ታመነ ስልጠናው በተለየ መልኩ የተሰጠ መሆኑን ተናግረው ስልጠናውን ለመስጠት ወደ ዩኒቨርሲቲው የመጡ የዱባይ ፖሊስ አመራርና አባሎችን አመስግነው ስልጠናው ከታህሳስ 14 ጀምሮ እስከ ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም መሰጠቱን ገልጸዋል። ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው በፖሊሳዊ ስነ ምግባራቸው የተመሰገኑና ከፍተኛ የሆነ የማወቅ ጉጉት የነበራቸው መሆኑን የተገለጸ ሲሆን ሰልጣኞችም ባስተላለፉት መልዕክት የወሰዱትን ስልጠና ተግባር ላይ ለማዋልና የተጣለባቸውን ሃላፊነት በተግባር በመወጣት ብሎም ለሌሎች በማስማር ተተኪ ለማፍራት እንደሚሰሩ ተናግረውው መሰል ስልጠናዎችም በቀጣይ ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

Ethiopian Police University Official Page

02 Jan, 18:50


ለአዲስ አበባ ከፍተኛና ስትራቴጅክ የፖሊስ አመራሮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ
ታህሳስ 24ቀን/2017 ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለበርካታ የፖሊስና የጸጥታ ተቋማትን አቅም ለማሳደግ ስራዎችን እየሰራ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ከፍተኛና ስትራቴጂክ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በዛሬው ዕለት ተጠናቋል፡፡
በስልጠና ማጠናቀቂያ ፕሮግራም ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት የስራ መመሪያ ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል አጠቃላይ እንደ ፌደራል ፖሊስ የተከናወኑ የለውጥና የሪፎርም ስራዎችን አስመልክቶ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን የአዲስ አበባ ፖሊስም ከለውጡ በኋላ ያሉ የለውጥና የሪፎርም ስራዎችን ይበልጥ ለማጠናከር በተለይም ከፍተኛ አመራሩን በስልጠና ማብቃትና ለሚመራቸው ብሎም ለሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ የወንጀል መከላከል ስራዎች ያግዘው ዘንድ ስልጠናው መሰጠቱ አስፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል ስልጠናውን በሚመለከት የስልጠና ሪፖርት ያቀረቡት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደረጀ አስፋው ስልጠናው በተመሳሳይ መልኩ ከዚህ በፊት ለፌደራል ፖሊስ ብሎም ለድሬደዋ ፖሊስ ከፍተኛና ስትራቴጂክ አመራሮች በተሰጠው ስልጠና መሰረት የተሰጠ ስልጠና መሆኑን ተናግረው አመራሮች በስልጠና ቆይታቸው በተግባርና በንድፈ ሃሳብ የተደገፉ በርካታ ስልጠናዎችን በተመረጡ ምሁራኖች የወሰዱ መሆናቸውን አስገንዝበው ስልጠናው ለቀጣይ ስራቸው ይበልጥ ስንቅ እንደሚሆናቸውና ሀገር ወዳድነት፣የኮሚንኬሽን ምንነትና አስፈላጊነት ብሎም የለውጥ አመራር ሚናዎች፣ ስነ ምግባር እና ሌሎች ስልጠናዎችን መውሰዳቸውን ጠቁመዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

29 Dec, 08:16


https://youtu.be/zYHmExFP4KM?si=YJhq3URiw1SX1oUA

Ethiopian Police University Official Page

26 Dec, 18:08


ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካል ደህንነት ጥበቃ አመራርና አባላት ስልጠና ተሠጠ
****
ታህሳስ 17/2017ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተከትሎ አሁን ካለው የግል ጥበቃ ዩኒቨርሲቲው ወደ ሚያስተዳድረው ጥበቃ እንዲዛወር ለማድረግ ለኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቀረበዉ ጥያቄ እና ይህንኑም ተግባር የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሀላፊነት ወስዶ እንዲሰራ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ፈተና ወስደው ላለፋ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአካል ደህንነት ጥበቃ አመራርና አባላት ስልጠና ተሰጥቷል።
ሰልጣኞች በስልጠና ቆይታቸው የተቋማት ደህንነት ጥበቃ፣ የተቋማት ደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ፣ የፍተሻ አሰራር ትምህርት፣ የስራ ስነ-ምግባርና ሌሎች ከሙያው ጋር ተያያዥነት ባላቸው ጉዳዮች ላይ ስልጠና ወስደዋል።
በስልጠና መርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ ማማከርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝደንት ም/ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሃኑ ስራችሁን በወትሮ ዝግጁነት በስነልቦና ፣ በቁርጠኝነት ፣በስነምግባር እና መረጃ መር በሆነ መንገድ የዩኒቨርስቲውን አከባቢ በንቃት በመመርመርና በማወቅ የዩኒቨርስቲውን ማህበረሰብና ተማሪዎች ደህንነታቸውን በመጠበቅ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ለሰልጣኞች መልዕክት አስተላልፈዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ም/ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶክተር ማቴዎስ ሙሉ በበኩላቸው ከዚህ ቀደም በተለያየ ሙያ ሀገራዊ ተልዕኮ ላይ ስትሳተፋ የቆያችሁ ቢሆንም ይህ የአካል ደህንነት ሙያ ለየት ያለ በመሆኑ በስልጠና ያገኛችሁትን እዉቀት በቅንነትና በታማኝነት በመስራት የተሰጣችሁን ትልቅ ሀላፊነት በትኩረት እንድትሰሩ ሲሉ መልክታቸዉን አስተላልፈዋል ።

Ethiopian Police University Official Page

26 Dec, 14:00


የዶክትሬት ዲግሪ ለማስጀመር በተዘጋጀ ሥርዓተ-ትምህርት ላይ ቫሊዴሽን ወርክሾፕ ተካሔደ።
*********
ታህሳስ 17/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሴኪዩሪቲ ስተዲስ እና በስትራቴጂክ ሴኪዩሪቲ ሊደርሺፕ የዶክትሬት ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራም ለማስጀመር ቀደም ብሎ በተዘጋጀው የሥርዓተ-ትምህርት ካሪኩለም ላይ የውስጥ ግምገማ ሲያደርግ ቆይቶ በዛሬው ዕለትም በዘርፋ ከፍተኛ ልምድ ያላቸው ከተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የመጡ ተመራማሪዎች በተገኙበት የውጭ ግምገማ የውይይት መድረክ አካሔዷል።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሀገራችንን የፖሊስ ሀይል በእውቀት በክህሎት በማሳደግ ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚሔድ ተቋም ለመፍጠር በመደበኛውና በተለያዩ አጫጭር ፕሮግራሞች ላይ አገልግሎቱን ማስፋት በሚችልበት ሁኔታ ላይ በስፋት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ም/ፕሬዝዳንት ረ/ኮሚሽነር ተሻለ ሚቆሬ ዩኒቨርሲቲው በትምህርት ዘርፋ በአሁኑ ጊዜ በሰባት ኮሌጆች እና በተለያዩ 38 የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን ተቀብሎ የፖሊስን ተልዕኮ ለማሳካት የሚሰራ ዩኒቨርሲቲ እንደሆነ ገልጸው ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፖሊስ የትምህርትና ስልጠና የልህቀት ማዕከል ለመሆን የያዘውን ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
አያይዘውም ለዶክትሬት ዲግሪ ተዘጋጅተው በቀረቡት ሁለት የሥርዓተ-ትምህርት ካሪኩለሞች ላይ ዛሬ የተካሔደው የውጭ ግምገማ የመጨረሻው እንደሆነ ተናግረው የተገኙትን ግብዓቶች በማካተት በቀጣይ ለሴኔት ቀርቦ እንደሚጸድቅ ተናግረዋል።

Ethiopian Police University Official Page

26 Dec, 09:24


https://youtu.be/loemxqBkMDA?si=jieIA71qnKxBE7Py

Ethiopian Police University Official Page

07 Dec, 15:45


የ25ኛ ዙር መደበኛ ሰርተፊኬት ዕጩ መኮንኖች የትክሻ ማዕረግ የማልበስ ፕሮግራም ተከናወነ
******
ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከመደበኛ ትምህርትና ስልጠና ባሻገር የፖሊስ አመራርና አባላት ሙያው የሚጠይቀውን የፖሊስ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማስቻል በረጅም ጊዜ እና በአጫጭር ስልጠናዎች የፖሊስ ሰራዊቱን አቅም የሚያሳድጉ ስልጠናዎችን በመስጠት የተሰጠውን ታላቅ ሀላፊነት በብቃት እየተወጣ ይገኛል።
ዩኒቨርሲቲው በአፖስቶ ካምፓስ የሚያሰለጥናቸውን የ25ኛ ዙር መደበኛ ሰርተፊኬት ዕጩ መኮንኖች የሪኩሪቲ ጊዚያቸውን ጨርሰው በትምህርትና ስልጠና እንዲሁም በስነ-ምግባር የትክሻ ማዕረግ (ስትራይፕ) ለመልበስ የሚያስችለውን መስፈርት ለአሟሉ ሰልጣኞች በዛሬው ዕለት የትክሻ ማዕረግ (ስትራይፕ) የማልበስ ፕሮግራም ተከናውኗል።
በፕሮግራሙ ላይ በመገኘት የስራ መመሪያ የሰጡት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የትምህርት ም/ፕሬዝዳንት ረ/ኮሚሽነር ተሻለ ሚቆሬ ዕጩ መኮንኖቹ ከስልጠናው ባሻገር በልማት ስራ ያከናወኗቸውን ስራዎች ተዘዋውረው በመጎብኘት በዚህ የአጭር ጊዜ ቆይታችሁ የሰራችሁት ስራ በናንተ ውስጥ ሰባዊነትን፣ ሙያዊ ብቃትና ምልዑነትን ያየንበት ስራ መሰራቱን ያየንበተት ነው ብለዋል።
አያይዘውም በዚህ የስልጠና ቆይታችሁ ማዕረግ ብቻ ሳይሆን ለማዕረጉ የሚመጥን እውቀት ይዛቹህ መውጣት ይገባል ሲሉ ለዕጩ መኮንኖቹ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በሌላ በኩል የስልጠና ሪፖርት ያቀረቡት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአፖስቶ ካምፓስ ተወካይ ሀላፊ ረ/ኮሚሽነር ካሳሁን ተስፋዬ በአፖስቶ ካምፓስ 925 ዕጩ መኮንኖች በስልጠና ላይ እንደሚገኙ ገልጸው የተቀመጠውን መስፈርት ያሟሉ 920 ዕጩ መኮንኖች የትክሻ ማዕረግ ለመልበስ እንደደረሱ ተናግረዋል።

Ethiopian Police University Official Page

07 Dec, 03:25


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የነጭ ሪቫን ቀን “ህጻናት የሚሉት አላቸዉ እናዳምጣቸዉ” በሚል መሪ ቃል ተከበረ
*
ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ35ኛ ጊዜ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ 19ኛ ጊዜ የተከበረው የነጭ ሪቫን ቀን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሴቶች እና ህፃናት ዋና ክፍል አዘጋጅነት “ህጻናት የሚሉት አላቸዉ እናዳምጣቸዉ” በሚል መሪ ቃል በትናንትናው ዕለት የዩንቨርሲቲው ሰራተኞች እና ተማሪዎች በተገኙበት ተከብሮ ውሏል ፡፡
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሰዉ ሃብት አስተዳደር ዋና ክፍል ሀላፊ ኮማንደር አሰፋ ገለቱ የነጭ ሪቫን ቀን በሴቶች እና ህፃናት ላይ የሚደረሰዉን ጥቃት ለመከላከል የሚደረገውን ትግል የበለጠ ለማጠናከርና ለማጎልበት የሚጠቅም መድረክ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሴቶች እና ሕጻናት ዋና ክፍል ተወካይ ም/ኮማንደር ጸዳለ አሰፋ በሀገርም ሆነ መዓለም አቀፍ ደረጃ የሴቶች እና ህፃናት ጥቃት እስካሁን ድረስ እንዳልቆመ እና ለዚህም የፖሊስ አመራሩ እና አባላት የሴቶች እና ህፃናት ሰባዊ መብትን በማክበር እና በማስከበር ህገ መንግስታዊ ኃላፊነታችንን መወጣት ይገባል ሲሉ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል ፡፡
በመጨረሻም በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የህግ እና ሰባዊ መብቶች ዋና ክፍል ኃላፊ እና የዩኒቨርሲቲዉ ነገረ ፈጅ ዕጩ ዋና ኢንስፔክተር ሲሳይ በሴቶች እና ህፃናት ሰባዊ መብት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት በጋራ መከላከል ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው በመጨረሻም እለቱን በማስመልከት የፓናል ዉይይት ተደርጓል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

03 Dec, 07:47


https://youtu.be/czehKsn0-7s?si=IrIZihjFQYfWUGV3

Ethiopian Police University Official Page

03 Dec, 03:14


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከቻይና የህዝብ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (cppu) ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሄደ
****
ህዳር 23 ቀን 2017ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አጋርነቱን በማጠናከር በሀገር ደረጃ የተጣለበትን የህዝብና የሀገር ሓላፊነት ይወጣ ዘንድ በዛሬው ዕለትም ይበልጥ ስራውንና አጋርነቱን ሊያጠናክሩና አብረው መስራትና መተባበር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ከቻይና የህዝብ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ውይይት ተካሂዷል፡፡
በውይይት ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ባደረጉት ንግግር ሁለቱ ሀገራት በበርካታ የትብብር ማዕቀፎች ለበርካታ አመታት በህዝብ ለህዝብ እንዲሁም በፀጥታ ተቋማት ዘርፈ ብዙ ተግባራትን ሲያከናውኑ የቆዩ መሆናቸውን በመናገር ውይይቱም ይህንኑ ተግባርና እንቅስቃሴ ይበልጥ ለማጠናከርና የበለጠ አጋርነቱን ለማስኬድ አጋዥ መሆኑን ለዕለቱ የክብር እንግዶች ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል በዕለቱ የተገኙት የቻይና የህዝብ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሊቀመንበር Mr pan ciping, (vice chairman of china peoples police university) የቻይና የህዝብ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሀገረ ቻይና አንጋፋ የፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ገልጸው ወደ አንጋፋው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መምጣታቸው ይበልጥ በቀጣይ ሁለቱ ዩኒቨርሲቲዎች አብረው ለመስራትና ለመተባበር እንዲሁም ዕውቀትን ለመጋራት ሚናው የጎላ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

02 Dec, 17:43


ለሁለተኛዉ ዙር የስትራቴጅክ የፖሊስ አመራሮች የአመራርነት ብቃት ስለጠና እየተሰጠ ነዉ
**
ህዳር 23/2016ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፌደራል ፤ከድሬደዋ እና አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ለተዉጣጡ የስትራቴጅክ የፖሊስ አመራሮች በሁለተኛዉ ዙር የአመራርነት ብቃት ማሳደጊያ ስለጠና እየተሰጠ ነዉ፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳዳርና ልማት ምክትል ፕሬዝደንት ምክትል ኮሚሽነር ጌቱ ተ/ዮሐንስ ስልጠናዉ ወጥ የሆነ የፖሊስ አገልግሎት ለመስጠት፤ ስትራቴጅክ የሆነ የአመራርነት ክህሎት ግንዛቤ ለመፍጠር እና የጋራ የሆኑ ጉዳዮች ላይ በመወያየትና ልምድ በመለዋወጥ በቂ እና ተቀራራቢ የሆነ አመለካከትና አስተሳሰብ እንዲኖር ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝደንት ረ/ኮሚሽነር ደረጀ አስፋዉ ስልጠናዉ ከፍተኛ ልምድ እና እዉቀት ባላቸዉ ሃላፊዎች እንደሚሰጥ ጠቅሰዉ የአመራርነት አቅምን ለማሳደግ ታልሞ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልጸዋል።

Ethiopian Police University Official Page

27 Nov, 15:30


በቻይና የወንጀል ምርመራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና ፕሮፌሰር, ዋንግ ሲ የተመራ የልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ጋር ውይይት አካሔደ።
*****
ህዳር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በቻይና የወንጀል ምርመራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና ፕሮፌሰር, ዋንግ ሲ የተመራ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት በትምህርትና ስልጠና በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮች ላይ ከዩኒቨርሲቲው ስትራቴጂክ አመራሮች ጋር ውይይት አካሒደዋል።
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ኢትዮጵያ እና ቻይና ለረጂም ጊዜ የቆየ ጠንካራ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላቸው አገሮች መሆናቸውን ገልጸው የፖሊስ ትብብር የጸጥታ አቅምን ለማሳደግ እና ቀጠናዊ ተግዳሮቶችን ለመፍታት ያለመ ስትራቴጂካዊ አጋርነትን በማጠናከር ዩኒቨርሲቲው በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በቻይና የወንጀል ምርመራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እና ፕሮፌሰር, ዋንግ ሲ(WANG CE) በተደረገላቸው አቀባበል ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበው የቻይና የወንጀል ምርመራ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ (CIPUC) ከ76 ዓመት በላይ ልምድ ያለው በወንጀል ምርመራ እና በፎረንሲክ ሳይንስ መስክ ባለሙያዎችን ለማሰልጠን በቻይና የህዝብ ደህንነት ሚኒስቴር ስር ያለ ከፍተኛ ዝና ያለው አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የፖሊስ ዩኒቨርሲቲ እንደሆነ ገልጸዋል።

Ethiopian Police University Official Page

26 Nov, 23:17


አህጉር አቀፍ የአፍሪካ የሰላም ጉባኤ ተሳታፊ ሚኒስትሮች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲጉብኝት አደረ
*
****
ህዳር 17 ቀን 2016 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
አህጉር አቀፍ የአፍሪካ የሰላም ጉባኤ ተሳታፊ ሚኒስትሮች እና የሰላምና ጸጥታ ተቋማት ኃላፊዎች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት በቅርቡ የተመረቀውን የፎረንሲክ ምርመራና የምርምር የልህቀት ማዕከልን እና በግንባታ ሂደት ላይ ያለውን ባለ አምስት ኮከብ የኢንተርናሽናል ፖሊስ ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ፕሮጀክትን እንዲሁም ሌሎች የተከናወኑ የሪፎርም ሥራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የጉብኝቱ ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ በፎረንሲክ ሳይንስ ኢንስቲትዩት የምርምር የልህቀት ማዕከል እና በDNA ላብራቶሪ ምርመራ እንዲሁም ቴክኖሎጂዎችን በማበልፀግ ረገድ የሠራቸው ድንቅ ተግባራት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሞዴል ሆነው እንደሚያገለግሉ ተናግረው በቀጣይ ከተቋሙ ጋር ተቀራርቦ ለመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ገልፀዋል።

Ethiopian Police University Official Page

25 Nov, 20:49


ለስትራቴጅክ የፖሊስ አመራሮች የአመራርነት ብቃት ስልጠና እየተሰጠ ነ
*
*
ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያዎች እና ከድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽን ለተውጣጡ ስትራቴጂክ የፖሊስ አመራሮች የአመራርነት ብቃት ስልጠና እየተሰጠ ነው።
ስልጠናው የከፍተኛ አመራሩን ብቃት በሚመጥን መልኩ የተዘጋጀ፣ በሀገራችን ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ፣ የስትራቴጂክ አመራሩን የአመራርነት ብቃት ለማሳደግና የጎንዮሽ ግንኙነትን በማጠናከር ወቅቱ የሚጠይቀውን ዘመናዊ የፖሊስ አገልግሎት ለመስጠት የተዘጋጀ መሆኑን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ልማት ምክትል ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጌቱ ተ/ዮሐንስ ገልጸዋል።
በስልጠናው የመክፈቻ ፕሮግራም ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ምክትል ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደረጀ አስፋው ስልጠናው በቂ ዕውቀትና ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች እና ኃላፊዎች የሚሰጥ መሆኑን በመጥቀስ ስትራቴጂክ አመራሩ ተመሳሳይ የሆነ አስተሳሰብና አመለከከት ይዞ ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ የሚያግዝ ስልጠና እንደሆነ ገልጸዋል።

Ethiopian Police University Official Page

21 Nov, 04:59


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ስልጠና ላይ ለሚገኙ አፖስቶ ካምፓስ ለሰልጣኞች ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን መከላከል የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ
***
ህዳር 12 ቀን 3/2017ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አፖስቶ ካምፖስ በስልጠና ላይ ለሚገኙ 25ኛ ዙር መደበኛ ሰርተፊኬት ዕጬ መኮንኖችን ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃትን በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በትናንትናው ዕለት ተሰጥቷል ።
ስልጠናው የተሰጠው በዩኒቨርስቲው የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ዋና ክፍል አዘጋጅነት ሲሆን ስልጠናው ይበልጥ ትብብርና በስልጠና ቆይታቸው በመተጋገዝ ስሜት ስልጠናቸውን ለማጠናቀቅ አጋዥ መሆኑ ተመላክቷል ።
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ዋና ክፍል ሀላፊ ተወካይ ም/ኢ/ር ስመኝ ዩኒቨርሲቲውሲ ይህንን ስልጠና ሲሰጥ በትልቅ ሀላፊነት መሆኑን ጠቁመው ሰልጣኞች ስልጠናውን በተገቢው መንገድ መከታተል እንደሚገባ ተናግረዋል ።
የስልጠናው ዋና አላማ ሴቶች በስልጠናም ይሁን በተለያዩ የስራ ክንውኖች ከወንዶች እኩል የተጣለባቸውን ሀላፊነት እንዲወጡና ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ተቋማዊ ለውጥ ለማምጣት ያለመ ከመሆኑም ባሻገር ዕጬ መኮንኖቹ ወደ ስራ ሲገቡ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ ያለመ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል።
እንዲሁም ሴቶችን በተቋም በማህበራዊ እንዲሁም በበርካታ በሀገራዊ ተግባራት ላይ እኩል የማሳተፍን አስፈላጊነት ጨምሮ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በተገቢው መንገድ የተወያዩ ሲሆን ለተግባራዊነቱ በጋራ ከወንዶች ጋር በመሆን እንዲሰሩ ተናግረዋል ።

Ethiopian Police University Official Page

19 Nov, 03:14


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የማዕረግ ሽግግር ስልጠና መስጠት ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሔደ
****
ህዳር 10/2017 ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከሚሰጣቸው መደበኛ ስልጠናዎች በተጨማሪ የቆይታ ጊዜቸውን የሸፈኑ የፖሊስ አመራሮችን ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያመጡ ከኢንሰፔክተር ወደ ዋና ኢንስፔክተር የማዕረግ ሽግግር ያለፋ አመራሮችን በመቀበል የስልጠና ማስጀመሪያ መርሀ ግብር አካሂዷል፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያ መርሀ ግብሩ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአመራርና አቅም ግንባታ ስልጠና ማዕከል መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ካሳሁን መኮንን ዩኒቨርሲቲው ስልጠናውን ለመስጠት በቂ ዝግጂት ማድረጉን በመጠቆም ሰልጣኞች ስልጠናውን ለመውሰድ ዝግጂት አድርገው እንደመምጣታቸው መጠን ፖሊሳዊ ዲስፕሊንንና ስነ ምግባርን ከግምት ውስጥ በማስገባት የተጣለባቸውን የተቋምና የሀገር ሃላፊነት እንዲወጡ አሳስበዋል፡፡
በሌላ በኩል ዩኒቨርሲቲው የፖሊሳዊ ስልቶችና አካል ብቃት ስልጠና ማዕከል መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ፍቃዱ ጉደታ ሰልጣኝ አመራሮች የሚሰጣቸውን ስልጠና በተገቢው መንገድ በዩኒቨርሲቲው ህግና ደንብ መሰረት ስልጠናቸውን እንዲወስዱ አሳስበዋል፡፡
አክለውም ሰልጣኞቹ በተለያዩ የስራ ክፍሎች ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ የሃላፊነት ስራዎች ላይ ያሳለፉ እንደመሆናቸው መጠን ስልጠናቸውን በሚወስዱበት ስዓትና ጊዜያት ሁሉ ለሌሎች ዕጩ መኮንኖች ተምሳሌት በመሆን ስልጠናቸውን እንዲወስዱ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በመጨረሻም ሁለቱም ሃላፊዎች ባስተላለፉት መልዕክት ስልጠናው ተጀምሮ አስኪጠናቀቅ ድረስ በትብብር መንፈስ የስልጠናውን ዓላማ ከግብ ለማድረስና ሰልጣኞችም ከስልጠናው በቂ ልምድና ተሞክሮ በመያዝ ለቀጣይ ስራቸው የሚያግዝ ስልጠና እንዲወስዱ እንደሚሰሩ ተናግረዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

19 Nov, 02:19


ለትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው
**
ህዳር 9/2017ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የህዝብ ትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች ለሶስተኛ ዙር ስልጠና እየሰጠ ነው።
በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ ማማከርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሀኑ ዩኒቨርሲቲው የሀገር ውስጥ የፖሊስ መኮንኖችን ለበርካታ ዓመታት ስልጠናዎችን በመስጠት እያስመረቀ ያለ አንጋፋ ዩኒቨርሲቲ ከመሆኑም ባሻገር ለውጭ ሀገር የፖሊስ መኮንኖች ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ተናገረው ሰልጣኝ አመራርና ባለሙያዎች የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ለመውሰድ ወደ ዩኒቨርሲቲው በመምጣታቸው ለስራቸው አገዥ ስልጠናዎችን እንደሚሆንላቸው ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም የትራንስፖርት ቁጥጥር ስራ ‹‹ትልቅ ሳይንስ›› ነው ያሉ ሲሆን ሰልጣኝ አመራርና አባሎች የሚሰጣቸውን ስልጠና በተገቢው እንዲከታተሉ ተናግረው በስልጠና ቆይታቸውም በሀገራችን የትራንስፖርት ቁጥጥር መመሪያዎችና የህግ ማዕቀፎች እና ስነ ምግባርን ጨምሮ በርካታ ስልጠናዎችን በተግባርና በንድፈ ሃሳብ ደረጃ እንደሚወስዱ ጠቁመዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

17 Nov, 01:05


የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከአፍሪካ ካሉ ምርጥ 5 የፖሊስ ተቋም ውስጥ አንዱ ለመሆን የያዘውን ተልዕኮ እየተወጣን ይገኛል-የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤልበፎረንሲክ ምርመራና ምርምር የልህቀት ማዕከል ምርቃት ላይ በአስተላለፋት መልዕክት “በ2022 ዓ.ም በአፍሪካ ካሉ ምርጥ 5 የፖሊስ ተቋም ውስጥ የሚመደብ ሙያ ብቃቱን ያረጋገጠ፣ አካታችና በህዝብ ታማኝ የሆነ ፣ ዘመናዊ ፖሊስ አገልግሎት ለመፍጠር በሰራናቸው ስራዎች የክልል ፖሊስን ጨምሮ አደረጃጀታችንን እና አሰራሮቻችንን በማሻሻል፣ የሰው ኃይላችንን በብቃት ፣ በስብዕና ፣በቁጥርና በተዋጽኦ ጭምር በመገንባት በግንኙነት አቅርቦት እና በቴክኖሎጂ አጠቃቀም ያለንን አቅም በማሳደግ ተልዕኳችንን እየተወጣን እንገኛለን″ ብለዋል።
በሀገራችን የፖሊስ ምርመራ አገልግሎት በንጉሱ ዘመን በ 1934 ዓ.ም አባ ዲና በሚል የተጀመረ ይሁን እንጂ እንዳመሰራረቱ ሳይሆን የወንጀል አፈፃፀም እያደገና እየተወሳሰብ እንደሚሄዱ ይህንን የሚመጥን የፎረንሲክ ምርመራ መሳሪያ፣ ሙያዊ ብቃት ያለው የሰው ኃይል ፣ ምቹ የስራ አካባቢና የስልጠና ማእከል ባለመኖሩ ለዜጎችን ሰባዊ መብት ጥሰትና ተቋሙም በማህበረሰቡ ዘንድ እምነትና ክብር ያጣ እንዲሆን አድርጎት ቆይቷል። በመሆኑም በሀገራችን የመጣውን ለውጥ ተከትሎ ክቡር የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ለፖሊስ ባስቀመጡት ፍኖተ ካርታ መሠረት ይህንን በአፍሪካ ትልቁን የፖሊስ የፎረንሲክ ምርመራና የምርምር ልህቀት ማዕከል ከነሙሉ ግብዓቱ ተገምቶ ለዛሬ ምረቃ በመብቃቱ መደሰታቸውን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገልጸዋል።

Ethiopian Police University Official Page

16 Nov, 18:22


https://www.facebook.com/100077758515468/posts/pfbid022cHjPWuoEFZ2Xturne7j1t57XCQCjJvB98cLiZf3AXJfGuWfRMaccuq3At98uAufl/?app=fbl

Ethiopian Police University Official Page

16 Nov, 18:16


በተሟላ ሁኔታ የዲጅታል ፎረንሲክ፣የDNA ምርመራ፣የአሻራ ምርመራ እና ልዩልዩ ወንጀሎችን መመርመር የሚያስችል ላብራቶሪ መገንባቱ የፌዴራል ፖሊስ ወደ ምንፈልገው ቁመና እየመጣ መሆኑን በተግባር የሚያሳይ፣ የሚመሰክር ስራ ስለሆነ መላው የፖሊስ አባላትና አመራሮች ለዚህ ታላቅ ስራ እንኳን ደስ ያላችሁ ለማለት እወዳለሁ-ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ሰንዳፋ በሚገኘው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ተገንብቶ በዛሬው ዕለት በተመረቀው የፎረንሲክ ምርመራና ምርምር ኢንስቲትዩት የልህቀት ማዕከል ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተሟላ ሁኔታ የዲጅታል ፎረንሲክ ፣ የአሻራ ምርመራ ፣ የDNA ምርመራ እና ልዩልዩ ወንጀሎችንና ኬሚካሎች መመርመር የሚያስችል ላብራቶሪ ተገንብቶ በዚህ ስፍራ ማየት በቀላሉ የምናየው ብቻ ሳይሆን የፌዴራል ፖሊስ ወደ ምንፈልገው ቁመና እየመጣ መሆኑን በተግባር የሚያሳይ፣ የሚመሰክር ስራ ስለሆነ ለመላው የፖሊስ አባላትና አመራሮች ለዚህ ታላቅ ስራ የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

Ethiopian Police University Official Page

13 Nov, 18:35


ለህዝብ ትራንስፖርትና ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች የሚሰጠው ሁለተኛ ዙር ስልጠና ተጀመረ
***
ህዳር 04 / 2017 ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ዘርፈ ብዙ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን ለተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ተቋማት በመስጠት ላይ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የህዝብ ትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች በመጀመሪያው ዙር ሲሰጥ የቆየውን ስልጠና በማጠናቀቅ ሁለተኛ ዙር የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በዛሬው ዕለት አስጀምሯል፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ በመገኘት የስልጠና ማስጀመሪያ መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ማማከርና ማህበረሰብ አቀፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሀኑ ዩኒቨርሲቲው በፖሊሳዊ ትምህርትና ስልጠናዎች በሀገራችን እንዲሁም በምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ለመሆን በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው የሀገራችንን የፖሊስ መኮንን ከማስተማርና ማሰልጠኑም ባሻገር ለበርካታ ሀገራት የፖሊስ መኮንኖች ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ መሆኑን ተናግረዋል
አክለውም ዩኒቨርሲቲው የሀገር ውስጥ ተቋማት የተጣለባቸውን የህዝብ ሃላፊነት በተግባር ይወጡ ዘንድ አሻራውን ስልጠናዎችንና ማማከሮችን እንዲሁም ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ እየተወጣ መሆኑንና የዚሁ አካል የሆነው ለከተማዋ ትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች የሚሰጠው ስልጠና አንዱ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በመጨረሻም ሰልጣኝ አመራርና ባለሙያዎች በዩኒቨርሲቲው የሚሰጣቸውን የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በተገቢው መንገድ በመከታተል ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ መልክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

13 Nov, 18:32


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለህፃናት ማቆያ ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ
*
ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሴቶች እና ህፃናት ጉዳይ ዋና ክፍል አዘጋጅነት ለህፃናት ማቆያ ለሚሰሩ የፅዳት ሰራተኞች እና ሞግዚቶች የመጀመሪያ ደረጃ የህክምና እርዳታ እና የህፃናት አመጋገብ፤ አያያዝ እና እንክብካቤ ላይ ያተኮረ በንድፈ ሃሳብ እና በተግባር የተደገፈ ስልጠና ለተከታታይ ሁለት ቀናት ተሰጥቷል፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራም ላይ የተገኙት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሰዉ ሀብት ስራ አመራር መምሪያ ኃላፊ አቶ አዳነ አስረስ የህፃናት ማቆያዉ የተቋቋመበት ዋናዉ አላማ የዩኒቨርሲቲዉ ሰራተኞች ተልኳቸዉን በአግባቡ ለመወጣት እንዲያስችላቸዉ በተገቢዉ መንገድ ይዞ ለመዝለቅ መሆንን ተናግረዉ ስልጠናዉ ትልቅ አላማ አለዉ ብለዋል፡፡
አክለዉም በንግግራቸዉ በተለያዩ ስልጠናዎች እዉቀታቸውን በየጊዜዉ የበለጠ እያሻሻላችሁ እና እያሳደጋችሁ እንዲሁም የሰለጠናችሁትን ስልጠና ወደ ተግባር ቀይራችሁ ጥሩ የህፃናት ማቆያን በመፍጠር ለፌደራል ፖሊስ አርዓያ መሆን ይገባችኋል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

13 Nov, 00:36


ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የህዝብ ትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ
****
ህዳር 03/2017ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ተቋማት የተጣለባቸውን ሀገራዊና የህዝብ ሃላፊነት ይወጡ ዘንድ በርካታ ስልጠናዎችን በመስጠት ላይ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የህዝብ ትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች ሲሰጥ የነበረው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተጠናቋል፡፡
በስልጠና ማጠናቀቂያ ፕሮግራሙ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ማማከርና ማህበረሰብ አቀፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሀኑ ዩኒቨርሲቲው ከሌሎች ተቋማት ልዩ የሚያደርገው የተቋማት አመራርና ሰራተኞች ለህዝባቸውና ለሀገራቸው ቅድሚያ በመስጠት ሃላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ በርካታ የስብዕናና የሞራል ግንባታ ስልጠናዎችን በመስጠት የሚታወቅ አንጋፋና የመጀመሪያ የሀገራችን የፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አክለውም ሰልጣኝ አመራርና ባለሙያዎቹ የሚሰሩት ስራ ከሰው ህይወት ጋር የተገናኘ በመሆኑ ስራቸውን በተገቢው መንገድ በመስራት እንዲሁም የትራንስፖርት ህግና መመሪያን መሰረት በማድረግ ለከተማው የህዝብ ትራንስፖርት ፍሰት በትጋት እንዲሰሩ መልዕክት በማስተላለፍ ዩኒቨርሲቲው ከተቋሙ ጋር በቀጣይ በበርካታ የስራ ሂደቶች በጋራ ለመስራት ዝግጁ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

09 Nov, 14:12


የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ የህዝብ ትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች ስልጠና መስጠት ጀመረ
****
ጥቅምት 30 02/2017ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ
ዩኒቨርሲቲው በሀገር ደረጃ የተጣለበትን የህዝብና የሀገር ሃላፊነት ከመወጣቱም ባሻገር በርካታ ትብብሮችንና አጋርነትን የሚያጠናክሩ ዘርፈ ብዙ ስልጠናዎችን ለበርካታ ተቋማት የማማከር ስራዎችን በመስጠት በዛሬው ዕለትም ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ የህዝብ ትራንስፖርት ቁጥጥር አመራርና ባለሙያዎች የሚሰጠውን የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና አስጀምሯል።በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ በመገኘት ስልጠናውን በሚመለከት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የምርምር፣ ማማከርና ማህበረሰብ አቀፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ዳንኤል ብርሀኑ ዩኒቨርሲቲው መሰል ስልጠናዎችን ሲሰጥ የመጀመሪያው አለመሆኑንና ሰልጣኝ አመራርና ባለሙያዎቹ ስልጠና ለመውሰድ ወደ አንጋፋው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ መምጣጣቸው ለቀጣይ ስራቸው አጋዥና አበረታች ስልጠና ለመስጠት ዩኒቨርሲቲው ሙሉዝግጂት ማድረጉን ተናግረዋል፡፡በሌላ በኩል ስልጠናውን በሚመለከት የስልጠና ማስጀመሪያ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሃላፊ እና የትራንስፖርት ጥናትና ቴክኖሎጂ ዘርፍ ሀላፊ አቶ ወርቁ ደስታ አንጋፋው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ስልጠናውን ለተቋሙ ሰራተኞች ለመስጠት ያደረገውን ጉልህ ሚና በማመስገን ለሰልጣኞች ከቅበላ ጀምሮ ላደረገው ስራ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

07 Nov, 22:17


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ኮሪያ የፀረ-ሙስና ፖሊሲዎች እና ስኬቶች አንፃር የኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና እና የኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂ በሚል ርዕስ የግማሽ ቀን ስልጠና ተሰጠ።
ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የደቡብ ኮሪያ ሪፐብሊከ የፀረ ሙስና እና የሲቪል መብቶች ኮሚሽን ምክትል ሊቀመንበር ክቡር ቹንግ ሱንግ የን የዩኒቨርሲቲው ስትራቴጅክና ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ከደቡብ ኮሪያ የፀረ-ሙስና ፖሊሲዎች እና ስኬቶች አንፃር የኢትዮጵያ የፀረ-ሙስና እና የኢኮኖሚ ዕድገት ስትራቴጂ በሚል ርዕስ የግማሽ ቀን ስልጠና ለአካዳሚክ ፣ለስታፍ ሰራተኞች እና ለተማሪዎች የግማሽ ቀን ስልጠና ሰጥተዋል።
የተሰጠው ስልጠና በደቡብ ኮሪያ የፀረ-ሙስና ትግል ውስጥ የኢትዮጵያን የፀረ-ሙስና ስትራቴጂዎች እና ምርጥ ተሞክሮዎችን በጥልቀት በመወያየት እና በባለሙያዎች መመሪያ ለመዳሰስ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
በሌላ በኩል በፕሮግራሙ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ም/ኮሚሽነር ጀኔራል መስፍን አበበ ኢትዮጵያ እና ኮሪያ ለረጅም ጊዜ የተለያዩ ስራዎችን በጋራ ሲሰሩ የቆዩ መሆናቸን ገልፀዉ ይህ ዛሬ የተሰጠው ስልጠና እንደ ሀገር መልካም አጋጣሚ እና ፀረ ሙስናን ለመከላከል የሚረዳ መሆኑን ገልጸዋል።

Ethiopian Police University Official Page

07 Nov, 18:21


በአሜሪካ የፍሎሪዳ አለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ የፎረንሲክ ሳይንስ ባለሙያዎች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው የልምድ ልውውጥ አደረጉ
****
ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በአሜሪካ የፍሎሪዳ አለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ የፎረንሲክ ሳይንስ ባለሙያዎች ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮችና፣በዩኒቨርሲቲው ከወንጀል ምርመራና ፎረንሲክ ሳይንስ ኮሌጅ አመራርና ባለሙያዎች ጋር የልምድ ልውውጥ አካሒደዋል።
በተካሔደው የልምድ ልውውጥም በትምህርትና ስልጠና፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም የፍሎሪዳ አለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲ ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የቁሳቁስ ድጋፍ በሚያደርግባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።
የልምድ ልውውጡ የተለያዩ ዘመኑ የደረሰባቸውን የወንጀል ምርመራ ላብራቶሪዎችን ጨምሮ ሌሎች የዕውቀት ሽግግር የአቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችንና የተለያዩ የተግባር ስልጠናዎችን በሚመለከት ያሉ ልምዶች ለኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ እንዲያጋሩ የተጠየቀ ሲሆን በቀጣይ በጋራ እና በትብብር እንደሚሰሩ ተገልጿል።
በተጨማሪም በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት እንግዶች ዩኒቨርሲቲው በወንጀል ምርመራና ፎረንሲክ ሳይንስ በኩል የያዘው አቅጣጫ የሚመሰገንና ወቅቱን የሚመጥን ተግባር መሆኑን በመናገር አጋርነትና ትብብሩን ይበልጥ በማጠናከር ዩኒቨርሲቲው ለያዘው የወንጀል መመርመርና መከላከል ስራ በወንጀል ምርመራና ፎረንሲክ ሳይንስ ኢንስቲትዩት በኩል የሚሰጠውን የትምህርትና ስልጠና ሂደት ለማገዝ የበኩላቸውን ድጋፍና ትብብር እንደሚያደርጉ ተናግረዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

05 Nov, 15:33


የዱባይ ፖሊስ ልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ አመራሮች ጋር ምክክር አካሔዱ
ጥቅምት 26 ቀን 2017 ዓ.ም
የዱባይ ፖሊስ ልዑካን ቡድን በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ከዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ም/ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ እና ምክትል ፕሬዝዳንቶች እንዲሁም ከፍተኛ አመራሮች ጋር በትምህርትና ስልጠና በጋራ ለመስራት የሚያስችል ምክክር አካሒደዋል፡፡
የዱባይ ፖሊስ ልዑካን ቡድን የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠውን ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ሀላፊነት አጠናክሮ እንዲያስቀጥል እና የወንጀል መከላከል አቅምን ለማሳደግ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በጋራ በመሆን ስልጠና መስጠት በሚችሉበት ጉዳይ ላይ መክረዋል፡፡
የልዑካን ቡድኑ አባላት ተቋሙ በለውጡ የፈጠራቸውን የቴክኖሎጂ አቅሞች እና እየተሰሩ ያሉ ፕሮጀክቶችን እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ስልጠና ለመስጠት ያለውን መሰረተ ልማቶች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

05 Nov, 15:24


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በማህበራዊ ፍርድ ቤት ላይ ለሚሰሩ አምራር እና አባላት ስልጠና ተሰጠ
****
ጥቅምት 26/2017 ዓ.ም በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በማህበራዊ ፍርድ ቤት ላይ ለሚሰሩ በሸገር ከተማ አስተዳደር የኩራጅዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት እና የበረክ ወረዳ ፍርድ ቤት ለተዉጣጡ አምራር እና አባላት ከመደበኛዉ ፍርድ ቤት ባሻገር ማህበረሰቡ ባሉበት አካባቢ ሁነዉ በቀበሌያቸዉ እና በከተማቸዉ በሚያዉቁት ቋንቋ ፤ ባህል፤ህግና ደንብ መሰረት በሽምግልና፤ በድረድር፤ በዕርቅና በግልግል የግጭት አፈታት ስነ-ስርዓት ላይ ያተኮረ ስልጠና ተሰጥቷል ::
በስልጠናዉ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት ም/ኮሚሽነር ጀኔራል መስፍን አበበ በማህበረሰቡ ዉስጥ በጥልቀት ዘልቆ በመግባት የሚያጋጥሙትን ችግሮች በመረዳት ግዴታችሁንና መብታችሁን አዉቃችሁ በትክክለኛዉ እና ሚዛናዊ በሆነ መንገድ ጸረ ሰላም የሆኑ ሃይሎችን ከህብረተሰቡ ለይተን በማዉጣት የከተማችንን ሰላም እና ድህንነት መጠበቅ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰዉ በተሰጣችሁ ስልጠና መሰረት ግጭቶች ሲፈጠሩ በሀቅ እና በእዉነተኛ መንገድ ትክክለኛ ፍርድ መስጠት ይገባችኋል ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል በስልጠናዉ ላይ የተገኙት የበረክ ወረዳ ፍርድ ቤት ፕሬዝደንት አቶ ገዳ አየለ ባህላዊ ፍርድ ቤት በእዉነተኛ መንገድ የመፍረድ እንደመሆኑ መጠን ስልጠናዉ ባህላችንንና ትዉፊታችንን የበለጠ በማጠናከር በህግ እና በደንቡ መሰረት ትልልቅ ስራዎችን ለመስራት የሚረዳ እና የበለጠ ዉጤታማ የሚያደርግ ስልጠና ነዉ ብለዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

02 Nov, 00:49


ለከፍተኛ አመራሮች ልዩ የቋንቋ ስልጠና የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ
***
ጥቅምት 22/2017ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሠንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከፈረንሳይ እና ከቻይና ኢምባሲ ጋር በመተባበር ፤ ከወንጀል መከላከል፤ ከወንጀል ምርመራ፣ ከፌደራል ማረሚያ ቤት እና ከፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለተዉጣጡ ከፍተኛ አመራሮች የቻይነኛ ፤የእንግሊዘኛ እና በፈረንሳይኛ ልዩ የቋንቋ ስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል፡፡
በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራሙ ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ም/ፕሬዝደንት ረ/ኮሚሽነር ደረጀ አስፋዉ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እንደ ተቋም በሪፎርሙ በርካታ ስራዎችን እያከናዎነ ሲሆን በተለይም የሰዉ ኃይል አቅም ግንባታ ላይ መሰረት በማድረግ ለፖሊስ አመራሮች እና አባሎች የተለያዩ የቋንቋ ስልጠናዎችን በመስጠት እንደ ተቋም ያለዉን ያለዉን ክፍተት ለመሙላት እየተሰራ መሆን ገልጸዉ ስልጠናዉ ለታለመለት አላማ እንዲዉል በንቃት እና በትኩረት መሳተፍ አለባችሁ ብለዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

01 Nov, 19:16


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው የቫሊዴሽን ወርክሾፕ ተጠናቀቀ
*
ጥቅምት 22/2017 ዓ/ም ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ተወዳዳሪ የፖሊስ መኮንኖችን አስተምሮ ለማብቃት የሚያግዙ ሞጁሎችን በማዘጋጀት ለተከታታይ ሶስት ቀናት ሲያካሂደው የነበረው የቫሊዴሽን ወርክሾፕ በዘሬው ዕለት ተጠናቀቀ፡፡
በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ዩኒቨርሲቲው ጠንካራና ተወዳዳሪ እንዲሁም ሳይንስን እና እውቀትን መሰረት ያደረገ የወንጀል መመርመርና መከላከል ስራን በተገቢው መንገድ በመስራት ወንጀልን ለመከላከል የሚተጉ የፖሊስ ዕጩ መኮንኖችን የማፍራት ተግባሩን ይበልጥ ለማጠናከር የሚያግዙ ሞጁሎችን ማዘጋጀትና ለተማሪዎች ሙሉ ዕውቀትን ለመስጠት ፕሮግራሙ እጂግ ወሳኝ እንደነበር ተናግረዋል፡፡
በሌላ በኩል በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ተሻለ ሚቆሬ መሰል የቫሊዴሽን ፕሮግራሞች ሲካሄዱ የመጀመሪያ አለመሆናቸውን ገልጸው ስራዎቹ የዩኒቨርሲቲውን የማስተማር አቅም ይበልጥ ለማሻሻልና ተወዳዳሪ የፖሊስ መኮንኖችን ለማፍራት አጋዥ መሆኑን እና ለተግባራዊነታቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት እንዲተባበሩ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ቫሊዳሽኑን ማብራሪያ የሰጡት በዩኒቨርሲቲው የወንጀል ምርመራና ፎረንሲክ ሳይንስ ኮሌጅ መምሪያ ሃላፊ ኢ/ር ዶክተር ሃጎስ ይሳቅ የቫሊዴሽን ወርክሾፕ ፕሮግራሙ በተያዘለት እቅድና አላማን መሰረት የተከናወነ መሆኑንና በፕሮግራሙ ላይ በቀረቡ ሞጁሎች በቂ እንዲሁም አስተማሪና እንዲሁም ክፍተቶችን በሚሞላ መልኩ መከናዎናቸውን በመናገር በአጠቃላይ 18 የተለያዩ ሞጁሎች መቅረባቸውንና በቀጣይ ለተግባራዊነታቸው በትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

30 Oct, 08:43


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የቫሊዴሽን ወርክሾፕ እየተካሔደ ነው
*******
ጥቅምት 20/02/2016ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጣቸውን የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራሞችን ይበልጥ ለማሻሻልና ለማጠናከር በትኩረት እየሰራ ሲሆን በዛሬው ዕለትም ለአይሲቲ ፣ሳይበር ደህንነት ፣የፎረንሲክ ሳይንስ እና የወንጀል ምርመራ በዲግሪ መርሃ ግብር (Modulare validation for Ict,cyber security, forensic science and crime investigation in degree programme) ላይ በወንጀል ምርመራና ፎረንሲክ ሳይንስ ኮሌጅ መምሪያ አዘጋጅነት ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የቫሊዴሽን ወርክሾፕ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ በመገኘት መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ዩኒቨርሲቲው የሚሰጠውን የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራሞችን ከሀገር ውስጥ ከሚሰጣቸው የፖሊስ የትምህርትና ስልጠና ፕሮግራሞች ባሻገር ለጎረቤት ሀገራት ጭምር በመስጠት ላይ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
አክለውም የአካዳሚክ ስራ ዩኒቨርሲቲው ለሚሰጣቸው የትምህርት ሂደቶች ድርሻው ከፍተኛ መሆኑንና የጋራ ትብብርንና መተጋገዝን የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን ፕሮግራሙ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ላስቀመጠው ራዕይና ተልዕኮ መሳካት እንዲሁም ያሉ ክፍተቶችን ለመሙላትና ብቁ እና ተወዳዳሪ ብሎም ለጎረቤት ሀገራት የፖሊስ የትምህርትና ስልጠና ተቋም ሆኖ ለትውልድ እንዲሻገር መሰል ስራዎችን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

25 Oct, 05:26


በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በሚካሄዱ ጥናታዊ ጽሁፎች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ የምክክር መድረክ ተካሄደ
***
ጥቅምት14/2016ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለበርካታ አመታት በርካታ ጥናታዊ ፅሁፎችን እያደረገ የመጣ አንጋፋ የሀገራችን የፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ለሚያከናውናቸው ጥናታዊ ፅኁፎች ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል ያስችለው ዘንድ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሂዷል፡፡
በምክክር ፕሮግራሙ ላይ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል መስፍን አበበ ባስተላለፉት መልዕክት የዩኒቨርሲቲው መምህራንና ምሁራኖች የዩኒቨርሲቲውን ራዕይና ተልዕኮ ከግብ ለማድረስ ዩኒቨርሲቲው በዋናነት ወቅቱን ያዋጀ በጥናትና ምርምር ላይ እንዲሁም በማማከርና ማህበረሰብ አቀፍ ዘርፎች ጭምር በርካታ ሂደቶችን ማከናዎን እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡
አክለውም ምክትል ኮሚሽነር ጀነራል ዩኒቨርሲቲው ለጥናትና ምርምር የሚያስፈልጉ አውዶችን ለመፍጠር በዩኒቨርሲቲው የሪፎርም ስራ መከናዎኑን በመናገር ሰዎች እንደየዝንባሌያቸውና እውቀትን ብሎም ካላቸው ተሞክሮ ጋር እንዲሰሩ በርካታ ስራዎች መከናዎናቸውን ተናግረዋል፡፡
በምክክርና ውይይት ፕሮግራሙ ላይ (consultation on the EPU Research practictices with phd holders, phd candidates,phd students) በተገኙበት ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ፕሮግራሙ በቀጣይ ዩኒቨርሲቲው ለሚያከናውናቸው የጥናትና ምርምር ሂደቶችን ከግምት ውስጥ ያስገባ እንደሆነ እና የዩኒቨርስቲውን የወደፊት የስልጠና እና የምርምር ዩኒቨርሲቲ ለማድረግ መስራት እንደሚገባ ውይይት ተካሂዷል፡፡

Ethiopian Police University Official Page

23 Oct, 13:03


የድሬዳዋ ፖሊስ አመራር እና አባሎች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት አደረጉ
****
ጥቅምት 13/2017 ዓ/ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
የድሬዳዋ ፖሊስ አመራር እና አባሎች በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት አዳዲስ ፕሮጀክቶች ፣የልማት ስራዎችን እና የህፃናት ማቆያ እንዲሁም ሙዚየምን በመዘዋወር ጉብኝት አድርገዋል ::
ከጉብኝቱ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ የዉጭ እና ህዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊ ኢንሰፔክተር ፍፁም ብርሃኑ የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ከተመሰረተበት ጊዜ ጀምሮ ያለውን ታሪካዊ ዳራ በሚመለከት ገለጻ አድርገውላቸዋል።

Ethiopian Police University Official Page

23 Oct, 12:39


ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ የፖሊስ አመራር እና አባላትን ፖሊሳዊ እውቀትና ክህሎት ለማሻሻልና ከመበደኛው መረሐ-ግብር በተጨማሪ በርቀትና ተከታታይ ትምህርት መረሐ-ግብር ተደራሽ ለማድረግ በቀን 23/01/2017 ዓ/ም በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የመግቢያ ፈተና መስጠቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም በአዲስ አበባ ፈተና ጣቢያ /ኮልፌ/ የተፈተናችሁ የፌደራል ፖሊስ አባላት የተሟላ መረጃ የሌላችሁ በመሆኑ ስማችሁ ከዚህ በላይ የተጠቀሰው ተፈታኞች በሙሉ የስራ አፈጻጸም፤ የአገልግሎት ጊዜ እና የትምህርት ደረጃችሁን የሚያሳይ ማስረጃ ከስራ ክፍለችሁ እስከ ጥቅምት15/2017 ዓ/ም ድረስ ብቻ ሰንዳፋ በሚገኘው የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ለርቀትና ተከታታይ ትምህርት ማዕከል በአስቸኳይ እንድታስልኩ ስንል እናሳውቃለን፡፡

Ethiopian Police University Official Page

20 Oct, 08:25


በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የወንጀልመከላከል ጠቅላይ መምሪያ አመራርና አባላት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት አደረጉ
ጥቅምት 2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ሰንዳፋ
በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከተለያዩ የወንጀልመከላከል ጠቅላይ መምሪያ የስራ ክፍሎች የተውጣጡ የፖሊስ አመራርና አባላት በኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲ ጉብኝት አድርገዋል።
በጉብኝታቸውም ስለዩኒቨርሲቲው አጠቃላይ ታሪክ እና አሁን ላይ በትምህርትና ስልጠና ፣በምርምር፣ በሰው ሀይል ግንባታ እና በማህበረሰብ አገልግሎት ስለሚያከናውናቸው ዘርፈ ብዙ ጉዳዮች ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን ዩኒቨርሲቲው የሚያስገነባቸውን አዳዲስ ፕሮጀክቶች ፣ሙዚየሙን ፣ የህፃናት ማቆየውን እና በአጠቃላ በተቋሙ እየተሰሩ ያሉ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።