የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media @addisababadiocese Channel on Telegram

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

@addisababadiocese


ይህ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ የቴሌግራም ቻናል ነው።
መንፈሳዊ አገልግሎትና ሰሞነኛ ጉዳዮች ይቀርቡበታል።
አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media (Amharic)

አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ማንኛውም ሴት ወዳጆችን ወይም እናቱን ለአምስት ነገሮች እና እንዚያ ሌሎች ምስጢርን በተለያዩ ትምህርት አቅርቦ ለመለያየት ይግባኝ። የሚከተለውን ምሽት ወደ ሚዲያ መምሪያ አገልግሎታዊ መረጃ ማህበረሰብ መከላከል የሚችሉትን መልክ በማሳየት ስለሚወዳድሩ ሃላፊነት አስተያየት አለበት። ይህን ሚዲያን ለመለየት ላይ ለእኛ ከተመሠረተው መለየት የገባና የአድማጮች፣ ሰዎች ለመሆን ያሰማሩን ለውጥ ቦታ፣ ታሪክ፣ ዜና፣ መረጃ፣ ስብከት እና ተጽኖአል። ከዚህ በተጨማሪም በግል እና በሚከተለው ኬክስ ውጪ እና ውጤታ ማሰብርተኛውን ስለ ጎሳ ሚዲያ ውጤቱን ይበልጥ እና በመለያየት አልተገኘም። ለመለየት ለእኛስ የሚከተሉትን መረጃዎችን እና ቋንቋ ፈንጂሮችን ትምህርትን፣ በቁጥጥም ዝርዝርዎችን ለማጻፍ ማስታወቂያ ስላለው ፔፍ ወይም ያግኙት በሚኖሩ ዩኒቴዎች ነፃ እንዳልሆን ሁሉ በተጨማሪ ከእኛ ጋር መረጃዎችን ይመልከቱ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

07 Feb, 16:59


አምላከ ተክለ ሃይማኖት ነፍሳቸውን በአጸደ ገነት ከአበው ቅዱሳን ጋር ያሳርፍልን፣

ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይሥጥልን

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

07 Feb, 16:59


ዜና ዕረፍት
#አምስት_ልጆቻቸውን_ለክህነት_ያበቁት_ቄሰ_ገበዝ_ታደሰ_ገ_ክርስቶስ_ከዚህ_ዓለም_ድካም_፸፫ ዓመታቸው ዐረፉ። ሥርዓተ ቀብራቸውም በደብረ ሊባኖስ ገዳም ተፈጸመ።

ጥር ፴/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

#አምስት_ልጆቻቸውን_ለክህነት_ያበቁት_ቄሰ_ገበዝ_ታደሰ_ገ_ክርስቶስ_ከዚህ_ዓለም_ድካም_፸፫ዓመታቸው ዐረፉ። ሥርዓተ ቀብራቸውም በደብረ ሊባኖስ ገዳም ተፈጸመ።

ቄሰ ገበዝ ታደስ ገ/ክርስቶስ ከአባታቸው ከመምህር ገ/ክርስቶስ ወ/ሕይወት እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ወርቅነሽ አስችሌ በ1944 ዓ.ም በደብረ ሊባኖስ ወረዳ ልዩ ስሙ ጸበል አፋፍ(ደብረ አስቦ) ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተወለዱ።

ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገ/ክርስቶስ እድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ በዚሁ በተወለዱበት ጸበል አፋፍ(ደብረ አስ ቦ) ከቤተ ሰቦቻቸው ጋር እየኖሩ በታለቁ ከደብረ ሊባኖስ ገዳም እየተመላለሱ ከየኔታ ወልደ ኢየሱ ስ ከፊደል ጀምረው ሙሉ ንባባትን ተምረዋል።

በመቀጠልም በዚሁ ገዳም ቅዳሴን ከነሙሉ አገባቡ እና አንቀጹ ከየኔታ ነቅዓ ጥበብ ደምሴ በሚገባ ተምረው በቅዳ ሴ መምህርነት ተመርቀዋል።
ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገ/ክርስቶስ ትምህርታቸውን ተምረው ካጠናቀቁ በኋላ ለአቅመ አዳም ሲደርሱ ሥርዓተ ጋብቻቸውን ከወ/ሮ እታለማሁ ወልደ ኪዳን ጋር በ1967/ዓ.ም በመፈጸም የሰባት ወንዶች እና የሶስት ሴቶች በድምሩ 10 ልጆችን የወለዱ ሲሆን 19 የልጅ ልጆችንም አይተዋል።
ከወለዷቸውም ልጆች መካከል አምስቱ የእርሳቸውን ዐሠረ ፍኖት በመከተል መንፈሳዊ ትምህርትን በሚገባ አስተምረው ለክህነት እንዲበቁ አድርገዋል።

ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገብረ ክርስቶስ በተማሩትም ትምህርት ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በሚገባ አገልግለዋል።

ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገ/ክርስቶስ እጅግ በጣም የተወደዱ ለሀገራቸውና ለሕዝባቸው ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ እድሜ ዘመናቸውን በሙሉ ለተቸገሩት ደራሽ ለተራቡት ሁሉ አጉራሽ በአካባቢው ማህበረ ሰብም ታዋቂ ስመ ጥር አስታራቂ ሽማግሌ አባት ነበሩ።
ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገ/ክርስቶስ በተወለዱበት አካባቢ በታላቁ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ችግር ሲፈጠር ፈጥነው በመድረስ የችግሩ ፈቺ በመሆን የሚታወቁ ታላቅ አባትም ነበሩ።
ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገ/ክርስቶስ በሥራቸው በአልግሎታቸው ሁሉ
እጅግ የተወደዱና የተመሰገኑ ከፈጣሪያቸው የተሰጣቸውን ጸጋ ተጠቅመው ያለፉ ስመ ጥር ነበሩ

ተወልደው ባደጉበት አካባቢ ከዲቁና ጀምረው ለብዙ ዘመናት እስከ ግብዝና ያገለገሉበት ደብር ወበሪ ዋሻ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ከብዙ ዓመታት በፊት ለግብር አገልግሎት ይጠቀምበት የነበረውና ተቋርጦ የነበረውን ትልቅ ዋሻ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውንና የጻድቁን ወዳጆች በማስተባበር የአውሬና የከብት መፈንጫ የነበረውን ዋሻ አጸድተው ለእይታ የሚማርክ ለየት ያለ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያን ዲዛይን አሠርተው ባለሶስት ጉልላት ያለው ቤተ መቅደስ አሠርተው ደብሩንም ወደ ገዳምነት አሰቀይረው ብዙ መናንያንና መነኮሳት እንዲኖሩበት አስደርገዋል።
ገዳሙም ራሱን የሚያስተዳድርበት የተለያዩ የልማት ሥራዎችን ሠርተው በማሠራት በጎ አድራጊዎችንም በማስተባበር ልዩ ልዩ ሥራዎችን ሠርተዋል።
በተጨማሪም የእመቤታችን የልደታ ለማርያም ታቦት ከአባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት ጋር በድርብነት ስትኖር የነበረችውን ጽላት በአካባቢው ማህበረሰብ ጥያቄ በ1991 ዓ.ም የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸውን እና በጎ አድራጊዎችን በማስተባበር ራሷን ችላ የማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን አሠርተዋል።
ይቺው ቤተ ክርስቲያን የተሠራችው በጭቃ በመሆኑና ያለችበትም ቦታ አመች ባለመሆኑ በረንዳው በጣም በመሰነጣጠቁ ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ አደጋ ላይ በመውደቁ በግብዝና የሚያገለግሏት ደብር ስትወድቅ ዝም ብዬ አላይም ብለው ከዛሬ 8 ዓመታት በፊት በልዩ ዲዛን እንድትሠራ በብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ መልካም ፈቃድ መሠረት አስጥለው ሥራው ተጀምሮ በአሁኑ ሰዓት ሥራው ጉልላት ላይ ደርሷል።
በዚሁ ደብር እመቤትችንን ጽዋዕ ሕይወትና ህብስተ አኮቴት በቤተ መቅደስ ሲመግባት የነበረውን የሊቀ መላእክት ቅዱስ ፋኑኤልን ፅላት በመልአኩና በእመቤታችን ወዳጆች ጥያቄ መሠረት ከእመቤታችን ጋር አብሮ እንዲሆን አስደርገዋል። በቦታውም ላይ ለሕሙማን ፈውስና ድህነትን የሚሰጥ ታምረኛ ጠበል በመፍለቁ ለሕዝበ ክርስቲያኑ አገልግሎት እንዲሰጥ አድርገዋል።
እንዲሁም ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገብረ ክርስቶስ አርሶ አደር ጠንካራ ካህን እንደመሆናቸው መጠን ደከመኝ ሰለቸኝን የማያውቁ በመሆናቸው የአብያተ ክርስቲያናት መብዛትና የሕዝበ ክርስቲያን መብዛት እጅጉን ስለሚያስደስታቸው ሕዝበ ክርስቲያኑም አምልኮተ እግዚአብሔር የሚፈጽምበት ቦታ እንዳይቸገር በማሰብ ከአባታችን ከአቡነ ተክለሃይማኖት ጋር በድርብነት ይኖር የነበረውን የቅዱስ ገብርኤልን ታቦት ልዩ ቦታው ጫጋል አፋፍ በሚባል ቦታ እንዲተከል አድርገዋል።
በዚሁ ቦታ ላይ ሕዝበ ክርስቲያኑን በማስተማርና በማስተባበር ከወበሪ ዋሻ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ተለይቶ ራሱን ችሎ የቅዱስ ገብርኤል ጽላት (ታቦት) በመትከል የአካባቢው ሕብረተ ሰብ በአቀረቡ እንዲገለገል አድርገዋል።
የአካባቢው ሕዝበ ክርስቲያንም በአቅራቢያው አገልግሎት እንዲያገኝ አድርገዋል።
ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገብረክርስቶስ ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎታቸው ጎን ለጎን ለአካባቢው ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ የሆኑ የልማት ሥራዎች ሠርተዋል።
ከእነዚህም መካከል ለአካባቢው ማህበረሰብ የንጹህ ውሃ መጠጥ ተጠቃሚ እንዲሆን ካለቸው ብርቱ ፍላጎት የተነሣ በብዙ ውጣውረድና እንግልት ንጹሕ የመጠጥ ውሃ እንዲያገኝ አድርገዋል።
የአካባቢው ማህበረሰብ ትልቁ ችግ የመንገድና የመብራትንም ጉዳይ ስለነበር ፤ ማህበረሰቡን በማስተባበር ጥግ አንባ የደረሰውን ጥርጊያ መንገድ እስከ ወበሪ ዋሻ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ድረስ በባለሙያ አስጠንተው ሥራው እንዲጀመር ብርቱ ጥረት እያደረጉ እያለ በሞት ተለይተዋል።

ለአሳነጹአት ለእመቤታችን ለማህደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን በብዙ ድካምና ልፋት በገደል ላይ መብራት ተስቦ እንዲገባ አድርገው የአካባቢውም ሕብረተ ሰብ ከጨለማ ወደ ብርሃን እንዲወጣ ያለሰለሰ ጥረት አያደረጉ ባለበት ሁኔታ በሞት ተለይተውናል።
ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገ/ክርስቶስ ለአካባቢው ሕብረተ ሰብ አድባር፣ ደግ፣ ርህሩህ፣ ቅን አሳቢ፣ ጸሎተኛ ትንሹን ትልቁን አክባሪ፣ ሥራ ወዳድ፣ ጠንካራ ፤አርሶ አደር ፤ካህን ነበሩ፣ የአካባቢውን ማህበረሰብ ለውጥ ጠዋት ማታ የሚናፍቁ እንቅልፍ የማይወስዳቸው ብርቱ አባት ነበሩ።

ቄሰ ገበዝ ታደሰ ገ/ክርስቶስ ባደረባቸው ድንገተኛ ሕመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ73 (በሰባ ሶስት) ዓመታቸው ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ውጣ ውረድ አረፉው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በቦሌ ደብረ ምህረት ቅ/ሚካኤል እና ጻድቁ አቡነ ጎርጎሪዮስ ቤ/ ክን የማህሌት አገልግሎት እና ጸሎተ ፍትሐት የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና ሊቃውንተ ቤ/ክርስቲያን በተገኙበት በደማቅ ሥነሥርዓት ሲከናወን አድሮ ጥር 28/2017 ዓ.ም ሥርዓተ ቀብራቸው በታላቁ በደብረ ሊባኖስ ገዳም የገዳሙ ጸባቴ አበው መንኮሳት ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከያተለያየ አድባራት እና ገዳማት በመጡ አስተዳዳሪዎች ሊቃውንቶች በተገኙበት ሥነ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

06 Feb, 19:45


#ጾመ_ነነዌን_ለሦስት_ቀናት_ከልኂቅ_እስከ_ደቂቅ_ሁላችንም_ጠዋትና_ማታበየቤተክርስቲያኑ_ዐውደ_ምሕረት_እየተገኘን_በንስሓ_በዕንባበጸሎት_በምህላ_የእግዚአብሔርን_ምሕረትናይቅርታ እንድንጠይቅ"

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ጾመ ነነዌን አስመልክተው ካስተላለፉት አባታዊ መልእክት የተወሰደ

ሰኞ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም የሚጀመረውን የፈጾመ ነነዌን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ ሰጥተዋል።

ሙሉ መልእክቱ እንደሚከተለው ቀርቧል

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባኤ፡-

‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)።

ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤

• የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !

እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣ አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን።

እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው።

በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን።

“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ”

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

ጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

01 Feb, 07:19


ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ለመነኮሳት ማረፊያ የሚያስገነባውን ባለ አምስት ወለል ሕንጻ(G+5) ግንባታ ባርከው አስጀመሩ።

ጥር ፬/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ለመነኮሳት ማረፊያ የሚያስገነባውን ባለ አምስት ወለል ሕንጻ(G+5) ግንባታ ባርከው አስጀመሩ።

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የምትገኘው የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ጥንታዊና ታሪካዊ ከሆኑት ገዳማት መካከል አንዷ ናት።

የገዳሟ አገልጋዮች አባቶች መነኮሳት በመሆናቸው ከተበታተነ ግላዊ ኑሮ ይልቅ በቤተ ክርስቲያኑ ቅጽረ ግቢ ውስጥ የጋራ ማረፊያ (በዓት) እንዲኖራቸው በማሰብ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ አማካኝነት የመነኮሳት ማረፊያ በ1961 ዓ/ም ተገንብቶ እስካሁን ሲጠቀሙበት መቆየቱን በገዳሙ 40 ዓመታት በላይ ያገለገሉት አገልጋይ አስታውሰዋል።

የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ መዊዕ አባ ገብረ ሥላሴ ጠባይ በበኩላቸው የሚሠራው ግዙፍ ሕንጻ ለመነኮሳት ማረፊያ ከመሆኑ በላይ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ ታሪክን ማስቀጠልና አሻራን ማኖር መሆኑን ገልጸዋል።

የሚገነባው G+5 የመነኮሳት ማረፊያ ሕንጻ በ6 ወራት ተገንብቶ እንደሚጠናቀቅ የተገለጸ ሲሆን ውሉን የወሰደው ላሜድ ኮንስትራክሽ በተባለው ጊዜ አጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ እንደሚያደርግ በብፁዕነታቸው ፊት ቃል ገብቷል።

አክለውም ገዳሟ በርካታ ኦርቶዶክሳውያን ተማጸነውባት በሕይወታቸው ዕረፍት ልባቸው መጽናናት ፈውስ ያገኙበት መሆኑን አስተውሰው በአባቶች መነኮሳት አስተባባሪነት የተደረገለት ሰው ሁሉ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

የአራዳ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሠናያት የቻለው ለማ በበኩላቸው የገዳሙ አስተዳደር ታሪክ ጠብቆና ለነገ ትውልድ የተላላፍን ሥራ ለመሥራት በመነሳቱ እጅግ የሚመሰገነው ያሉ ሲሆን በተለይም መንግሥት እየተገበረው ካለው የኮሪደር ልማት አንጻር የሚሠራው ሕንጻ ቦታ መጠበቁ ለመነኮሳቱ ማረፊያነት ማገልገሉ እንዳለ ሆኖ ለአካባቢው ድንቅ ውበት በመሆን እንደሚያገለግል ተናግረዋል።

ቀጥለውም ገዳሙ ሕንጻውን ሠርቶ ለማጠናቀቅ የተያዘው የ6 ወራት ዕቅድ በእጅጉ የሚደነቅ እንደሆነም ገልጸዋል።

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ታሪክ ለማስቀጠል የቤተ ክርስቲያንን ሀብት ለመጠበቅ የተደረገው መልካም ሥራ ያደነቁ ሲሆን በዚህም የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ መዊዕ አባ ገብረ ሥላሴንና ማኅበረ መነኮሳቱን አመስገነዋል።

አክለውም ግንባታው የተጀመረው የመነኮሳት ማረፊያ G+5 ሕንጻን በ6 ወራት ለማጠናቀቅ ዕቅድ መያዙ በእጅጉ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው ቦታው ተዳፋት ያለው ከመሆኑ አንጻር ሥራው ጥራትና በጥንቃቄ እንዲመራ አሳስበዋል።

በሐመረ ኖኅ በጥቶ ያልተማጸናና መልስ ያላገኘ አይኖርም ያሉት ብፁዕነታቸው በዚህ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ ታሪካዊ አሻራ ሁሉም እንዲሳተፍ ተስፋቸውን ገልጸዋል።

በቤተ ክርስቲያናችን በልማት ሥራዎችና የተለያዩ ክትትል የሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ አሠራሩ መስተካከል ይገባዋል ያሉት ብፁዕነታቸው የቤተ ክርስቲያንን ክብር የምእመናን ታዛዥነንት የካህናት አገልግሎት ታሳቢ በማድረግ ወደ ፊት መጓዝ አለብን ብለዋል።

ለዚህ ሀገረ ስብከቱ በሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት የሚገኘውን ሕጋዊ ቦታ በባለሙያዎች አስጠንቶ ለአምልኮ፣ለመቃብር እና ለልማት በሚል አቅጣጫ በማስቀመጥ ለማስተግበር በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታውሰው የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም አስተዳዳርና መነኮሳት በራሳቸው ተነሳሽነት ይህን ሕንጻ ለመሥራት መነሳታቸው ለነገ የመሥራት ማሳያ ነው በማለት ገልጸዋል።

የእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም የመነኮሳት ማረፊያ G+5 ሕንጻ መሠረት ድንጋይ ባለፈው ዓመት በብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ ተባርኮ መቀመጡ የሚታወስ ነው።

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

29 Jan, 18:00


#በዓለ_ዕረፍታ_ለሶልያና
የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍት ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገርጅ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል በድምቀት ተከበረ ።

#ጥር ፳፩/፳፻፲፯ ዓ/ም #የአዲስ_አበባ_ሀገረ_ስብከት_ሚዲያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

08 Jan, 15:33


በዓለ ልደትን አስመልክቶ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር በነገው ዕለት ይከናወናል።

በመሆኑም በነገው ዕለት ጥር ፩/፳፻፲፯ ዓ/ም በተዘጋጀው የቅዱስነታቸው የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ላይ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ከጥዋቱ 3:00 ጀምሮ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን።

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳዳር ዋና ክፍል

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

06 Jan, 21:48


እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ።
የበረከት በዓል ይሁንልን።

#የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ታኅሣሥ ፳፱/፳፻፲፯ ዓ/ም

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

06 Jan, 20:38


ቀጥታ ሥርጭት ከቅዱስ ላሊበላ

በየዓመቱ የሚከበረው የጌታችን አምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት ጸሎተ ማኅሌት ከደብረ ሮሐ ቅዱስ ላሊበላ ውቅር አብያተ ክርስቲያናት

ከአሚኮ የተወሰደ

ታኅሣሥ ፳፰/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሳችሁ።
https://www.facebook.com/share/v/1AmBm4KKuR/

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

06 Jan, 18:27


“#እግዚአብሔር ሕዝቡን በአሁኑ ላይ መቶ እጥፍ ይጨምር”
— ፩ኛ ዜና ፳፩፥፫

ሁለተኛው የእእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር
በአዲስ አበባ ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል

እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም በጤና አደረሳችሁ።
የበረከት በዓል ይሁንልን።

ታኅሣሥ ፳፰/፳፻፲፯ ዓ/ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

05 Jan, 20:20


የኢትዮጵያዊ ጃንደረባው ትውልድ ማኅበር የጌታችንን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደትን አስመልክቶ የሚያዘጋጀው #የአእላፋት ዝማሬ መርሐ ግብር በነገው ዕለት ታኅሣሥ ፳፰/፳፻፲፯ ዓ/ም በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል ይከናወናል።

የጌታን ልደት ምክንያት በማድረግ የሚዘጋጀው የእላፋት ዝማሬ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል በዚህ ዓመት ሲካሔድ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን በድሬዳዋ ከተማ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑ ተጠቁሟል።

የአእላፋት ዝማሬ በልደቱ ወቅት ከመላእክትና ከእረኞቹ አልፎ እንስሳት ትንፋሻቸውን ለገበሩለት ጌታ በልደቱ በተደሰተ ልብ በኦርቶዶክሳዊ ቃና ለበረከት በእምነት ምስጋና ለማቅረብ የተዘጋጀ መርሐ ግብር እንደሆነ ተገልጿል።

በአዲስ አበባ ቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም የሚከናወነው መርሐ ግብር ከቀኑ 10:00 በመሐረነ አብ ጸሎት የሚጀምር ሲሆን እስከ ምሽቱ 2:30 ይቆያል ተብሏል።

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

05 Jan, 17:54


ሕፃን ኄራኒ ተሾመ እና ሶልያና ተሾመ የመዝገበ ጸሎት መጽሐፍን በብሬል አዘጋጅተው አስመረቁ !

ታኅሣሥ ፳፯ /፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በሁለቱ ሕፃናት የተዘጋጀው መዝገበ ጸሎት በብሬል የተሰኘው የጸሎት መጽሐፍ በዛሬው ዕለት የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ የተከናወነ ሲሆን በዓለ ልደትንም አስመልክተው የስጦታ መርሐ ግብር አካሂደዋል።
ሁለቱ ታዳጊዎች ይህንን የጸሎት መጽሐፍ ለማዘጋጀት ከ 1 ዓመት በላይ እንደፈጀ እና ለመጽሐፉ ግብዓትነት ከሚውሉ መገልገያዎች ጀምሮ በብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ ማለፋቸውን የገለጹ ሲሆን በአሁኑ ወቅት መጽሐፉም በሊቃውንት ጉባኤ ተገምግሞ የእውቅና ሰርተፍኬት ማግኘታቸው ገልጸዋል።
'በእነዚህ ሁለት ልጆች የተሰራው ሥራ እጅግ የሚያስመሰግን በመሆኑ ከጎናቸው ልንሆን ይገባናል" በማለት ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተናገሩ ሲሆን መጽሐፉንም በመባረክ የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱን አከናውነዋል።
በዕለቱን ቀሲስ ዶክተር መዝገቡ ካሳ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ምክትል አካዳሚክ ዲን ቃለ ወንጌል የሰጡ ሲሆን በተጋባዥ ዘማርያን ፣በድጋፍ እና እንክብካቤ የአካል ጉዳተኞች ትምህርት ቤት ዝማሬዎች ቀርበዋል።
በዕለቱ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ ምክትል አካዳሚክ ዲን ቀሲስ ዶክተር መዝገቡ ካሳ፣ጥሪ የተደረገላቸው ካህናት፣ የኪነ-ጥበብ ባለ ሙያዎች፣ጥሪ የተደረገላቸው ምእመናን ተገኝተዋል። ለዚህ የጸሎት መጽሐፍ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የእውቅና እና የማበረታቻ ሰርተፍኬት ተበርክቶ መርሐግብሩ ተጠናቋል።

©️ተ.ሚ.ማ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

01 Jan, 16:35


በዓለ ልደትን አስመልክቶ ከባሕርዳር ወደ ላሊበላ የቀጥታ በረራ እንደሚኖር ተገለጸ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓልን ምክንያት በማድረግ ከባሕርዳር-ላሊበላ እና ከላሊበላ-ባሕርዳር የቀጥታ በረራ አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገለጸ።

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል በቅዱስ ላሊበላ በልዩ ድምቀት እንደሚከበር የሚታወስ ነው።
FMC
🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

01 Jan, 13:30


"ከሠተ አፉሁ ወልሳኑ ነበበ
አእኮቶ ወባረኮ ለእግዚአብሔር
መልዐ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ተክለ ሃይማኖት" ዚቅ ዘታኀሣሥ ተክለ ሃይማኖት

እንኳን ለታኅሣሥ ፳፬ ጻዱቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ልደት አደረሳችሁ።

የጻድቁ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን።

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

01 Jan, 06:54


ሰላም ለዳዊት ትሕትናሁ ሶበ ርዕየ
ወየውሀቶ ፍጹመ ዘአልቦ እከየ
እግዚአብሔር ይቤ እንዘ ይነብብ ሰደየ
እምነ ሕዝብየ አልዓልኩ ኅሩይየ
ወረከብክዎ ለዳዊት ገብርየ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

29 Dec, 17:45


ሲሳይ በገና የዜማ መሣሪያዎች ማሠልጠኛ ተቋም ከ100 በላይ ተማሪዎችን አስመረቀ።

ታኅሣሥ ፳/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ሲሳይ በገና የዜማ መሣሪያዎች ማሠልጠኛ ተቋም በዛሬው ዕለት የዜማ መሣሪያ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ያስመረቀ ሲሆን የማሰልጠኛው ኃላፊ የሆኑት ሊቀ ልሳናት መምህር ሲሳይ ደምሴ በዛሬው ዕለት ተቋሙ ለ10ኛ ጊዜ ተማሪዎችን እንዳስመረቀ የገለጹ ሲሆን በዛሬው ዕለትም 78 የበገና፣23 የክራር፣5 የመሰንቆ እና 1 የዋሽንት በአጠቃላይ 107 ተማሪዎች ማስመረቃቸውን ገልጸዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ በተመራቂ ተማሪዎች የዝማሬ አገልግሎት የተሠጠ ሲሆን የሲሳይ በገና የዜማ መሣሪያዎች ማሠልጠኛ ተቋም የ 11 ዓመት ቆይታን በተመለከተ የተቋሙ መሥራች እና ኃላፊ የሆኑት ሊቀ ልሳናት መምህር ሲሳይ ደምሴ ገለጻ አድርገዋል።

በዕለቱ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ም/ፕሬዚዳንት ፕ/ር አባ ኃይለ ገብርኤል ግርማ ፣ ጥሪ የተደረገላቸው የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ የተመራቂ ተማሪ ወላጆች በተገኙበት የምርቃት መርሐ ግብሩ ተከናውኗል። ©ዘገባው ተዋሕዶ ሚዲያ ማእከል ነው።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

29 Dec, 17:43


በሲዳማ ክልል በትራፊክ አደጋ ምክንያት ከ63 ሰዎች በላይ ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ ።

ታኅሣሥ ፳/፳፻፲፯ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በሲዳማ ክልል በቦና ዙሪያ ወረዳ በጋላና ወንዝ ድልድይ ላይ በደረሰው የመኪና አደጋ የ63 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ።

በሕይወት የተረፉትን በቦና አጠቃላይ ሆስፒታል የህክምና እረዳታ እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የክልሉ መንግሥት ኮምኒኬሽን ቢሮ ገልጿል።

ቸሩ እግዚአብሔረ ነፍሶቻቸውን በቸርነቱ እንዲቀበልልን ለቤተሰቦቻቸውም መጽናናቱን እንዲሰጥልን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ይመኛል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

29 Dec, 12:18


ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስነታቸው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ክብረ አበውን የጠበቀ አቀባበል አደረጉላቸው።

ታኅሣሥ ፳/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ ቅዱስነታቸው ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ክብረ አበውን የጠበቀ አቀባበል አደረጉላቸው።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርኦሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ከብፁዓን አባቶች ጋር የታኅሣሥ ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓልን ምክንያት በማድረግ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ታኅሣሥ ፲፯/፳፻፲፯ ዓ/ም ማቅናታቸው የሚታወስ ነው።

ቅዱስነታቸው ለሐዋርያዊ አገልግሎት ወደ ሥፍራው ካቀኑ ጀምሮ ምዕመናን ማስተማርና ቡራኬ መስጠቱ እንዳለ ሆኖ የጌቴሴማኒ ቤተ ደናግል የእናቶች ገዳም የሕጻናት ማሳደጊያን በመጎብኘት አባታዊ ቃለ በረከትና ቡራኬ ሰጥተዋል።

ቀጥለውም በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት የተገነቡ የራስ አገዝ ልማት ሥራዎችንና ሕንጻዎች ባርከው አገልግሎት እንዲሰጡ አድርገዋል።

በመጨረሻም የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓልን በቁልቢ በመገኘት ትምህርተ ወንጌልና ቡራኬ ስጥተው በዛሬው ዕለት ወደ ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተመልሰዋል።

ቦሌ ዓለም አቀፍ ማረፊያ እንደደረሱ በብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከብፁዓን አባቶች ጋር በመሆን እንደ በቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓት ቅዱስ ወንጌል ይዘው አቀባበል አድርገውላቸዋል።
ፎቶ፦የኢኦተቤ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

29 Dec, 09:26


በካራና አየር ጤና አካባቢ የሚገኘው ባሕረ ጥምቀት ቦታ ለበዓሉ ዝግጁ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

ታኅሣሥ ፳ /፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በካራና አየር ጤና አካባቢ የሚገኘው ባሕረ ጥምቀት ቦታ ለበዓሉ ዝግጁ ለማድረግ እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው ይህ ባሕረ ጥምተቅ ቦታ በበዓሉ የ11 አብያተ ክርስቲያናት ታቦታት የሚያድሩበት እንደሆነም ተገልጿል።

ይሁን እንጂ የባሕረ ጥምቀት ቦታውን ለአገልግሎቱ ምች ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የአብያተ ክርስቲያናቱ ትብብር አነስተኛ መሆኑን የአካባቢው ወጣቶች በትናንትናው ዕለት በቦታውን ተገኝተው ጉብኝት ላደረጉት ለሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አሳስበዋል።

ለበዓሉ ለማድረስ የተሠራ ያለው የታቦታት ማለፈያ ድልድል አብያተ ክርስቲያናቱና ምእምናን በማቴሪያል (ቁሳቁስ) ድጋፍ የአስቸኳይ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥያቄ አቅርበዋል።

ክቡር ሥራ አስኪያጁም ሥራው የሚያስመስግን መሆኑን ጠቅሰው በአስቸኳይ ከአብያተ ክርስቲያናቱ ሰበካ ጉባኤ አስተዳዳር ጽ/ቤት ጋር በመነጋገር አፋጣኝ የትብብር ድጋፍ እንዲደረግ መምሪያ እንደሚያስተላልፉ ገልጸዋል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

29 Dec, 08:23


በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እያካሔደ ነው።
ታኅሣሥ ፳/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ እያካሔደ ነው።

በጉባኤ ላይ ብፁዕ አቡነ ቀሌምጦስ የመንበረ ፓትርያርክ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ መምህር ጸጋ ወልደ ትንሣኤ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዋና ሐላፊ፣ የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ዋና ክፍል ሐላፊ መምህር ደምስ የአንድነቱ ተቀዳሚ ሰብሰባ ላእከ ኄራን መንክር ግርማ የየክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንደነት ሥራ አመራርና ተወካዮች የሁሉም ገዳማትና አድባራት ሰንበት ትሞህርት ቤቶች ሰብሳቢዎች ተገኝተዋል።
በጉባኤው የዓመቱ ሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ የተገኙ መልካም ውጤቶችና ክፍተቶችን መሠረት በማድረግ ውይይት እንደሚደረግ ይጠበቃል።

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት ከ600,000 በላይ ብዛት ያላቸው ሰንበት ተማሪዎች እንደሚገኙ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

05 Dec, 09:32


የምርቃት መርሐ ግብር ጥሪ
ታኅሣሥ 6/2017 ዓ/ም በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል

ከ6,000 በላይ ተማሪዎች ይመረቃሉ።

©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

30 Nov, 16:31


#ኅዳር ጽዮን ማርያም

የኅዳር ጽዮን ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ዮቴክ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያም እና አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሥራ ሐላፊዎች እንዲሁም የገዳማት እና አድባራት አስተዳዳሪዎች በርካታ ሊቃውንት እና ምዕመናን በተገኙበት ተከብሯል።

ፎቶ ዲ/ን ቅዱስ ጥበቡ

ኅዳር ፳፩/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

11 Nov, 18:57


ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደብረ ከዋክብት ዳጋ እስጢፋኖስ አንድነት ገዳምን ጎበኙ።

ኅዳር ፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ፣ የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት እየተገነቡ ያሉ ሕንፃ አብያተ ክርስቲያናትንና የደብረ ከዋክብት ዳጋ እስጢፋኖስ አንድነት ገዳምን ጎብኝተዋል።

በማስከተልም አብያተ ክርስቲያናቱን በኃላፊነት የሚያስገነቡትን አስተዳዳሪዎችንና መሐንዲሶችን ማወያየታቸው ተገልጿል፡፡

አዲስ በመገንባት ላይ ያለውን የደብረ ከዋክብት ዳጋ እስጢፋኖስ አንድነት ገዳምን የጎበኙት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የማጠናቀቂያ ሥራው በቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት መሠራት እንዳለበት መመሪያ ሰጥተዋል፡፡

ብፁዕነታቸው አክለውም ስለሀገራችን ኢትዮጵያ እና ስለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አንድነትና እድገት በበለጠ አብዝተው መጸለይ እንዳለባቸው ለገዳሙ አረጋውያን መነኮሳት አባቶች መልእክት አስተላልፈዋል ሲል የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ሕዝብ ግንኙነት የሀገረ ስብከቱን ሕዝብ ግንኙነት ክፍል ዋቢ አድርጎ ዘግቧል፡፡

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

11 Nov, 11:40


የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ፩ኛውን ሀገረ ስብከት አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ መደበኛ ጉባኤ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አዳራሽ በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ኅዳር ፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በጉባኤው በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ርእሰ መንበርነት እየተካሄደ ነው።

በጉባኤ የሀገረ ስብከቱ እና የክፍላተ ከተማ የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በሸገር ከተማ የሚገኙ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና የሰበካ ጉባኤ ምክትል ሊቃነ መናብርት ተሳትፈውበታል።

የየክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ዓመታዊ ሪፖርቶችም እየቀረቡ እኝደሚገኙም የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ዘገባ ያመለክታል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

09 Nov, 13:37


በአሪና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ሲሰጣቸው የነበሩ 784 አዳዲስ አማንያን በኦርቶደክሳዊ ጥምቀት ከብረው የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን ማግኘታቸው ተገለጸ።
መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ነው።

ጥቅምት ፴/፳፻፲፯ ዓ/ም

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

07 Nov, 10:36


የቅዱስ አማኑኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግኽምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል። ተሚማ

ጥቅምት ፳፰/፳፻፲፯ ዓ/ም

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

06 Nov, 16:42


የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጥንተ ስቅለቱ በቱሉ ዲምቱ መርሶ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከብሮ ዋለ!!

ጥቅምት ፳፯ /፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ሥር በሚገኘው በቱሉዲምቱ መርሶ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤ/ክ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ዝክረ ጥንተ ስቅለቱ በድምቀት ተከብሮ ዋለ።

በመርሐግብሩ ላይ አባቶች ካህናትና የደብሩ የሰንበት ት/ቤት አባላት የዕለቱን በዓል የተመለከተ ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል።

የደብሩ አስተዳዳሪ ክቡር ሊቀ ካህናት ለይኩን ደሴ በክብረ በዓሉ ላይ ለተገኙት ምእመናን በሙሉ የእንኳን በሰላም አደረሳችሁና በሰላም መጣችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

"አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ" (2ኛ ቆሮ ሰዎች 5፥14) በሚል የመጽሐፍ ቅዱስ ቃል መነሻነት ባህታዊ ገብረመስቀል ሰፋ ያለ ትምህርት ሰጥተዋል።

አያይዘውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሞተው ስለመተላለፋችን መሆኑን ገልጸው በእርሱ የደም ዋጋ የተገዛን መሆናችንን ዘወትር ልናስተውል ይገባል ሲሉ በአጽንኦት መክረዋል።

እርሱ ስለ እኛ በመስቀል ተላልፎ የተሰጠበት ምክንያት ከዘለዓለም ሞት ሊያድነን፤ ከኃጢአት በሽታ ሊያክመን፤ ብርሃን ሊሆንልንና የዘለዓለም ሕይወት ሊሰጠን መሆኑን በሰፊው አስተምረዋል። ከእኛ የሚጠበቀው በእምነት፣በተስፋ፣በፍቅርና በንስሐ ሕይወት መመላለስ እንደሆነም አያይዘው ገልጸዋል።

ደብሩ ስለሚያሠራው አዲስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በሕንጻ አሠሪ ኮሚቴ በኩል ለምእመናን ማብራሪያና ገለጻ ተደርጓል።

መረጃው የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ነው!!!

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

01 Nov, 20:32


ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ለኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ላበረከተችው ውጤታማ ታላቅ ድጋፍ የምስጋና ስጦታ ተበረከተላት።

ጥቅምት ፳፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ለኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ላበረከተችው ውጤታማ ታላቅ ድጋፍ የምስጋና ስጦታ ተበረከተላት።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ ፓትርያሪክ ልዩ ጽ/ቤት በአካል በመገኝት ቤተ ክርስቲያኒቱ ለኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ላበረከተችው ታላቅ ድጋፍ እንዲሁም ለሰጠችው ጥበብ የተሞላበት የአመራር አገልግሎት ከፍያለ ምስጋና በማቅረብ የክብር ምስጋና ስጦታ አበርክተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በወቅቱ ባስተላለፉት መልዕክት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትሪያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት እና የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ ጥበብ የተሞላበት አመራር እና ምክር በመደገፍ በርካታ የሰላም ሥራዎች መሠራታቸውን ገልጸው። በቅዱስነታቸው ድጋፍ እና የቅርብ ክትትል ቤተ ክርስቲያኒቱ ላበረክተችው የላቀ አስተዋፃኦ እጅግ አድርገን እናመሰግናለን በማለት የተዘጋጀውን የክብር ምስጋና ስጦታ በታላቅ አክብሮት ለቅዱስነታቸው አበርክተዋል፡፡

በመቀጠልም የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ በበኩላቸው ቤተ ክርስቲያኒቱን ወክለው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ከሆኑበት ጊዜ ጀምሮ በቅዱስነታቸው ጸሎት እና የቅርብ ክትትል አባል የሃይማኖት ተቋማቱን በማስተባበር የወከለቻቸውን ቤተ ክርስቲያን የሚያስከበር ሥራ ለመስረት የተቻላቸውን ጥረት እንዳደረጉ አብራርተዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የሃይማኖት ተቋማት የሥራ ሐላፊዎች ተገኝተዋል ሲል የጉባኤው ሕዝብ ግንኙነት ዘግቧል።

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

01 Nov, 05:36


ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲን የመማር ማስተማሩንና የማስፋፊያ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ።
©የዩኒቨርሲቲው ሕዝብ ግንኙነት

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

01 Nov, 05:34


የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተገለጸ።

ጥቅምት ፳፩/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በሶሪያ ኦርቶዶክስ ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተገለጸ።

ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ.ኤ.አ ሐምሌ 22 ቀን 1929 ዓ.ም ቡቸንክሩዝ በተባለ የሕንድ ግዛት የተወለዱ ሲሆን እ.ኤ.አ ከሐምሌ 26 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የምትተዳደረውን የሕንድ ቤተ ክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በሊቀ ጵጵስና መርተዋል።

ብፁዕነታቸው በዕድሜና በሕመም ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዕረፍት በማድረግ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አመሻሽ ላይ በሕንድ ኮቺ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

31 Oct, 13:30


የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ ሰንብቷል፡፡
ምልዓተ ጉባኤው ልዑል እግዚአብሔርን አጋዥና መሪ በማድረግ ስለ ቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት፣ ስለምጣኔ ሀብት እድገት፣ በሀገራችን እየተከሰቱ ስላሉት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች፣ ስለ ሀገር ሰላምና አንድነት፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደርና ሐዋርያዊ ተልእኮ ስለ ሰው ልጅ ሁሉ ደኅንነት በስፋት በመወያየት ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር ጠቃሚ የሆኑ ውሳኔዎችን
አሳልፏል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-
1. ከጥቅምት 4 ቀን እስከ ጥቅምት 9 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የተካሄደው ዓለም አቀፍ ጉባኤ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ 43ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ተሳታፊዎች የቀረበው ቃለ ጉባኤና የአቋም መግለጫ በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አህጉረ ስብከት የበጀት ዓመቱ የሥራ መመሪያ እንዲሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡
2. በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች እየተከሰተ ባለው የሰላም እጦት፣ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት የሰው ሕይወት እየተቀጠፈ፣ አካል እየጎደለ፣ ማኅበራዊ ትሥሥር እየተናደ፣ ሰብአዊ ክብር እየተጎዳ፣ መብት እየተጣሰ፣ በዜጎች ላይ ሥጋትና አለመረጋጋት እየበዛ ሀብትና ንብረት እየወደመ ስለሆነ ጉዳዩ አስቸኳይ መፍትሔ የሚያስፈልገው መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ ስለሆነም በጦርነትና በግጭት የመጣ ሰላም፣ የተገነባ ሀገር የለምና በሀገራችን እያጋጠመ ያለውን ችግር ለመፍታት ካለፈው በመማር በጥበብ፣ በማስተዋልና በሰለጠነ አካሄድ በሰላማዊ መንገድ በመወያየት ችግሩ በእርቅ እንዲፈታ ለሁሉም ወገኖቻችን ቅዱስ ሲኖዶስ የሰላም ጥሪውን በአጽንኦት ያቀርባል፡፡
3. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና በሥሩ ባሉ ገዳማትና አድባራት ውስጥ እየቀረቡ ያሉ መጠነ ሰፊ የአስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ ለማድረግ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጀምሮ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት፣ በክፍላተ ከተሞችና ችግር አለባቸው ተብለው በጥናት በሚለዩት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ላይ የማጣራት ሥራ እንዲሠራና ውጤቱ ለውሳኔ እንዲቀርብ በሦስት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡
4. የኦሲኤን ቴሌቪዥን ስርጭት የተቋረጠ በመሆነ በአዲስ መልክ ሁሉንም የአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ተናጋሪዎች ማህበረሰብ ባቀፈ መልኩ አገልግሎት እንዲሰጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአፋን ኦሮሞ ኔትወርክ በሚል ስያሜ በጠቅላይ ቤተ ክህነት በኩል ውል ተፈርሞ በአዲስ መልክ የሳተላይት ግዥ እንዲፈጸም ሆኖ አስተዳደሩን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኛ ብዙኃን ድርጅት ጋር በአንድ ሊቀ ጳጳስና ቦርድ ራሱን በቻለ ሥራ አስኪያጅ እየተመራ አገልግሎቱ ከነበረው በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ቅዱስ
ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

5. የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለደቀ መዛሙርት የሚሰጠው የምስክር ወረቀት አድቫንስ ዲፕሎማና ዲግሪ እንዲሆን ሥርዓተ ትምህርቱ ለሚሰጠው የትምህርት ማስረጃ በሚመጥን መልኩ ተሟልቶ፣ ሊኖረው የሚገባው የሰው ኃይል በየዘርፉ ተጠናክሮ ወደ ትግበራ እንዲገባ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፣
6. የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በሥነ ሕንጻና በኪነ ጥበብ በዓለም ደረጃ ከፍተኛ አድናቆትና ክብር የሚሰጠው ከመሆኑ በተጨማሪ በመዐርገ ጵጵስና ፕትርክና የሚሾሙ አባቶች ሥርዓተ ሲመት የሚፈጸምበት፣ ጥንታዊና ታሪካዊ ካቴድራል መሆኑን ታሳቢ በማድረግ ለዕድሳት ሥራው የገንዘብ ድጋፍ እንዲደረግለት ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤ በተጨማሪም ምእመናን እስከ አሁን እንደሚያደርጉት ሁሉ ለእድሳት ሥራው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ቅዱስ ሲኖዶስ
ያሳስባል፡፡
7. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዐቢይ ኮሚቴ ሥራውን አጠናክሮ እንዲቀጥልና በንቃት እንዲሳተፍ ሁሉንም አህጉረ ስብከት ባቀፈ ሁኔታ የአጀንዳ መረጣና ተሳታፊ የመለየት ሥራ እንዲከናወን ሆኖ ዐቢይ ኮሚቴው የሥራ ዕቅዱንና አፈጻጸሙን ለቋሚ ሲኖዶስ እያቀረበ በማስወሰን እንዲሠራ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

በአጠቃላይ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንፈስ ቅዱስ እየተመራ ላለፉት ተከታታይ ቀናት በመንፈሳዊ፣ በማኀበራዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ተገቢውን ውሳኔ በማስተላለፍ መደበኛ ስብሰባውን በዛሬው ዕለት በጸሎት አጠናቅቋል፡፡ መሐሪና ሁሉን ቻይ የሆነ እግዚአብሔር አምላካችን ለሀገራችን፣ ለሕዝባችን፣ ለዓለሙ ሁሉ ሰላሙን፣ ፍቅሩንና አንድነቱን ይስጥልን፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ
ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም
ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ጥቅምት ፳፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም.
ኢትዮጵያ አዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

31 Oct, 10:11


ለ፲ ቀናት በዝግ ሲካሔድ የቆየው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ ከሰዓት በሚሰጠው መግለጫ እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ።

ጥቅምት ፳፩/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

ለ፲ ቀናት በዝግ ሲካሔድ የቆየው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ ከሰዓት በሚሰጠው መግለጫ እንደሚጠናቀቅ ተገለጸ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት መሠረት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ በጥቅምት 12 እና በግንቦት ርክበ ካህናት (የትንሣኤ 25ኛ ቀን) ይካሔዳል።

በዚህ ዓመት የጥቀምት ቅዱስ ሲኖዶስ መልዐተ ጉባኤ ከጥቅምት 12/2017 ዓ/ም ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ሲካሔድ የቆየ ሲሆን ዛሬ ከሰዓት በሚሰጠው የጉባኤ መግለጫ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።

የዚህ ዓመቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ በ28 አጀንዳዎች ሲወያይ መቆየቱም ታውቋል።

የጉባኤውን የቀን ውሎና ውሳኔዎች በተመለከተም በመጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሥራ አእኪያጅና የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ አማካኝነት መረጃዎች ለተመልካች ሲደርሱ መቆየታቸው የሚታወስ ነው።
🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

30 Oct, 08:40


በወላይታ ዞን በካዎ ኮይሻ ወረዳ በመሬት መንሸራተት አደጋ #የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ።

ጥቅምት ፳/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በወላይታ ዞን በካዎ ኮይሻ ወረዳ 01 ቀበሌ እና ኮይሻ ላሾ ላይ በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ በሰው ህይወትና ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ የወረዳው አስተዳደር አስታውቋል።

በወረዳው በሁለቱም ቀበሌ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ 2 ወንድ 5 ሴት በድምሩ 7 ሰው የሞቱት ሲሆን አንድ ወንድና አንድ ሴት ላይ ከባድ የአካል ጉዳት አድርሷል ሲል የዎላይታ ዞን ኮምኒኬሽን ዘግቧል።

#እግዚአብሔር አምላክ ነፍሶቻቸውን በቸርነቱ እንዲቀበላቸው ለወዳጅ ዘመድም መጽናናትን እንዲሰጥልን የአዲስ አበባሀ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ይመኛል።

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

22 Oct, 18:42


የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

ጥቅምት ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

በየዓመቱ ጥቅምት 12 ቀን የሚጀምረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ቃለ በረከት ተከፍቷል።

የምልዐተ ጉባኤውን ውሎ ምን ይመስል እንደነበር መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው የቅዱስ ሲኖዱስ ም/ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለኢኦተቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ድርጅት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ አባ አብርሃም እንዳሉት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ድንጋጌ መሠረት እየተካሔደ የሚገኘው የቅዱስ ሲኖዶሶ ምልዐተ ጉባኤ ከሰዐት በፊት በነበረው ስብሰባ ሰባት ብፁዓን አባቶች በአባልነት የተካተቱበት አጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙን ገልጸዋል።

ምልዐተ ጉባኤው ከሰዓት በኋላ በነበረው ስብሰባ አርቃቂ ኮሚቴው በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት የተለዩትንና ሌሎች አጀንዳዎችን በመለየት ለምልዐተ ጉባኤው በማቅረብ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ጉባኤው ማጽደቁን አብራርተዋል።

ምልዐተ ጉባኤው አያይዞም በተራ ቁጥር አንድ ላይ የተቀመጠው አጀንዳ የተመለከተ ሲሆን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጉባኤ መክፍቻ ቃለ በረከትን የዓመቱ የቤተ ክርስቲያናችን የአገልግሎት መመሪያ እንዲሆን ጉባኤው መወሰኑንም መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው ገልጸዋል።

በመጨረሻም ጉባኤው ነገ ሲቀጥል የቅዱስ ሲኖዶስ #የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናና ሕልውና በተመለከተ ፣ #የ43ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሪፖርት እንዲሁም #ሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ውይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

22 Oct, 13:50


የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በትናንትናው
የእሳት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች አጋርነቱን ገለጸ።

ጥቅምት ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በትናንትናው የእሳት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች አጋርነቱን ገለጸ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስቅዱስ ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ፡ም በአዲስ አበባ ከተማ መርካቶ ገበያ ሸማ ተራ በተባለው አካባቢ በደረሰው የእሳት አደጋ ጉዳት ለደሰባቸው ወገኖች ባስተላለፉት መልእክት በደረሰው የሃብትና ንብረት ውድመት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸው።

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች እንዲፅናኑ እና የሕይወት ውጣ ውረድ አካል መሆኑን በመረዳት ከጉዳታቸው ለማገገም በተስፋ እንዲነሳሱ አደራ ብለዋል።

የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ላይ ሆነው የቃጠሎውን አደጋ በመስማታቸው ለሁሉም ተጎጂዎች የማጽናኛ መልእክት ማስተላለፋቸውን ዋና ሥራ አስኪያጁ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስቅዱስ ገልፀዋል።

በአደጋው ተጎጂ የሆኑ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በተለይም ክርስቲያኖች በመተባበር ክርስቲያናዊ ምግባር እንዲያሳዩ ዋና ሥራ አስኪያጁ አሳስበዋል።

መንግሥትና ኅብረተሰቡ በመልሶ ማቋቋም ሥራ ለሚያደርጉት ጥረት ሀገረ ስብከቱ የበኩሉን እንደሚወጣ እናስታውቃለን ብለዋል።

መረጃውን ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ነው።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

22 Oct, 11:16


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በመጀመሪያ ቀን ጉባኤው አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሠይሟል።

#የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የጥቅምት 2017 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ጉባኤውን ማካሔድ ጀምሯል።

በዚህ በዛሬው ከሰዓት ቀፊት በነበረው ጉባኤ ሰባት ብፁዓን አባቶች አባላት ያሉበትን አጀንዳ አርቃቂ ኮሜቴ ሠይሟል።

በዚህም መሠረት
1.ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

2.ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

3.ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

4.ብፁዕ አቡነ ማርቆስ
በሰሜን አሜሪካ ሲያትል አይዳሆ ኦሪገን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

5.ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ
የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት

6.ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ
የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ

7.ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ
የሶማሌ ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ መሆናቸውን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ በጥቅምትና በግንቦት ርክበ ካህናት እንደሚካሄድ ይታወቃል።

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

5,537

subscribers

9,627

photos

27

videos