የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

@addisababadiocese


አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

22 Oct, 18:42


የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

ጥቅምት ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።

በየዓመቱ ጥቅምት 12 ቀን የሚጀምረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ቃለ በረከት ተከፍቷል።

የምልዐተ ጉባኤውን ውሎ ምን ይመስል እንደነበር መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው የቅዱስ ሲኖዱስ ም/ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለኢኦተቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ድርጅት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ አባ አብርሃም እንዳሉት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ድንጋጌ መሠረት እየተካሔደ የሚገኘው የቅዱስ ሲኖዶሶ ምልዐተ ጉባኤ ከሰዐት በፊት በነበረው ስብሰባ ሰባት ብፁዓን አባቶች በአባልነት የተካተቱበት አጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙን ገልጸዋል።

ምልዐተ ጉባኤው ከሰዓት በኋላ በነበረው ስብሰባ አርቃቂ ኮሚቴው በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት የተለዩትንና ሌሎች አጀንዳዎችን በመለየት ለምልዐተ ጉባኤው በማቅረብ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ጉባኤው ማጽደቁን አብራርተዋል።

ምልዐተ ጉባኤው አያይዞም በተራ ቁጥር አንድ ላይ የተቀመጠው አጀንዳ የተመለከተ ሲሆን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጉባኤ መክፍቻ ቃለ በረከትን የዓመቱ የቤተ ክርስቲያናችን የአገልግሎት መመሪያ እንዲሆን ጉባኤው መወሰኑንም መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው ገልጸዋል።

በመጨረሻም ጉባኤው ነገ ሲቀጥል የቅዱስ ሲኖዶስ #የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናና ሕልውና በተመለከተ ፣ #የ43ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሪፖርት እንዲሁም #ሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ውይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል ብለዋል።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

22 Oct, 13:50


የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በትናንትናው
የእሳት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች አጋርነቱን ገለጸ።

ጥቅምት ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በትናንትናው የእሳት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች አጋርነቱን ገለጸ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስቅዱስ ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ፡ም በአዲስ አበባ ከተማ መርካቶ ገበያ ሸማ ተራ በተባለው አካባቢ በደረሰው የእሳት አደጋ ጉዳት ለደሰባቸው ወገኖች ባስተላለፉት መልእክት በደረሰው የሃብትና ንብረት ውድመት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸው።

በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች እንዲፅናኑ እና የሕይወት ውጣ ውረድ አካል መሆኑን በመረዳት ከጉዳታቸው ለማገገም በተስፋ እንዲነሳሱ አደራ ብለዋል።

የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ላይ ሆነው የቃጠሎውን አደጋ በመስማታቸው ለሁሉም ተጎጂዎች የማጽናኛ መልእክት ማስተላለፋቸውን ዋና ሥራ አስኪያጁ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስቅዱስ ገልፀዋል።

በአደጋው ተጎጂ የሆኑ ወገኖችን መልሶ ለማቋቋም በሚደረገው ጥረት ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በተለይም ክርስቲያኖች በመተባበር ክርስቲያናዊ ምግባር እንዲያሳዩ ዋና ሥራ አስኪያጁ አሳስበዋል።

መንግሥትና ኅብረተሰቡ በመልሶ ማቋቋም ሥራ ለሚያደርጉት ጥረት ሀገረ ስብከቱ የበኩሉን እንደሚወጣ እናስታውቃለን ብለዋል።

መረጃውን ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ነው።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ /Addis Ababa Diocese Media

22 Oct, 11:16


የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በመጀመሪያ ቀን ጉባኤው አጀንዳ አርቃቂ ብፁዓን አባቶችን ሠይሟል።

#የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

የጥቅምት 2017 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ጉባኤውን ማካሔድ ጀምሯል።

በዚህ በዛሬው ከሰዓት ቀፊት በነበረው ጉባኤ ሰባት ብፁዓን አባቶች አባላት ያሉበትን አጀንዳ አርቃቂ ኮሜቴ ሠይሟል።

በዚህም መሠረት
1.ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

2.ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

3.ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

4.ብፁዕ አቡነ ማርቆስ
በሰሜን አሜሪካ ሲያትል አይዳሆ ኦሪገን ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

5.ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ
የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት

6.ብፁዕ አቡነ ኤጲፋንዮስ
የምሥራቅ ጉራጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ

7.ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ
የሶማሌ ጅግጅጋ ሀገረ ስብከት ጳጳስ መሆናቸውን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ገልጿል።

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ በጥቅምትና በግንቦት ርክበ ካህናት እንደሚካሄድ ይታወቃል።

🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚🎚

#ስለአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን"

#ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
#መረጃ ጥቆማ
[email protected] ይጠቀሙ።
በፌስቡክ https://www.facebook.com/AddisAbabaDiocese?mibextid=2JQ9oc

ከዚህ በተጨማሪ በሌሎች የበይነ መረብ አማራጮች ለመከታታል
በቴሌግራም: https://t.me/AddisAbabaDiocese
በዋትስ አፕ: https://whatsapp.com/channel/0029VaJznc90rGiNUScgwn3U
በዩቱዩብ: http://www.youtube.com/@AddisAbabaDioceseMedia
በቲውተር: https://twitter.com/AADioceseMedia/media
በቲክቶክ:http://tiktok.com/@mediaofaadiocese
መጠቀም ይችላሉ።

5,531

subscribers

8,583

photos

22

videos