የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ጥቅምት ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በየዓመቱ ጥቅምት 12 ቀን የሚጀምረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ቃለ በረከት ተከፍቷል።
የምልዐተ ጉባኤውን ውሎ ምን ይመስል እንደነበር መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው የቅዱስ ሲኖዱስ ም/ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለኢኦተቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ድርጅት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ አባ አብርሃም እንዳሉት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ድንጋጌ መሠረት እየተካሔደ የሚገኘው የቅዱስ ሲኖዶሶ ምልዐተ ጉባኤ ከሰዐት በፊት በነበረው ስብሰባ ሰባት ብፁዓን አባቶች በአባልነት የተካተቱበት አጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙን ገልጸዋል።
ምልዐተ ጉባኤው ከሰዓት በኋላ በነበረው ስብሰባ አርቃቂ ኮሚቴው በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት የተለዩትንና ሌሎች አጀንዳዎችን በመለየት ለምልዐተ ጉባኤው በማቅረብ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ጉባኤው ማጽደቁን አብራርተዋል።
ምልዐተ ጉባኤው አያይዞም በተራ ቁጥር አንድ ላይ የተቀመጠው አጀንዳ የተመለከተ ሲሆን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጉባኤ መክፍቻ ቃለ በረከትን የዓመቱ የቤተ ክርስቲያናችን የአገልግሎት መመሪያ እንዲሆን ጉባኤው መወሰኑንም መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው ገልጸዋል።
በመጨረሻም ጉባኤው ነገ ሲቀጥል የቅዱስ ሲኖዶስ #የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናና ሕልውና በተመለከተ ፣ #የ43ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሪፖርት እንዲሁም #ሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ውይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል ብለዋል።
ጥቅምት ፲፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
የጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በየዓመቱ ጥቅምት 12 ቀን የሚጀምረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ዛሬ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ቃለ በረከት ተከፍቷል።
የምልዐተ ጉባኤውን ውሎ ምን ይመስል እንደነበር መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው የቅዱስ ሲኖዱስ ም/ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ለኢኦተቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ድርጅት ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ አባ አብርሃም እንዳሉት በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ድንጋጌ መሠረት እየተካሔደ የሚገኘው የቅዱስ ሲኖዶሶ ምልዐተ ጉባኤ ከሰዐት በፊት በነበረው ስብሰባ ሰባት ብፁዓን አባቶች በአባልነት የተካተቱበት አጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙን ገልጸዋል።
ምልዐተ ጉባኤው ከሰዓት በኋላ በነበረው ስብሰባ አርቃቂ ኮሚቴው በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት የተለዩትንና ሌሎች አጀንዳዎችን በመለየት ለምልዐተ ጉባኤው በማቅረብ 28 የመወያያ አጀንዳዎችን ጉባኤው ማጽደቁን አብራርተዋል።
ምልዐተ ጉባኤው አያይዞም በተራ ቁጥር አንድ ላይ የተቀመጠው አጀንዳ የተመለከተ ሲሆን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጉባኤ መክፍቻ ቃለ በረከትን የዓመቱ የቤተ ክርስቲያናችን የአገልግሎት መመሪያ እንዲሆን ጉባኤው መወሰኑንም መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም ገረመው ገልጸዋል።
በመጨረሻም ጉባኤው ነገ ሲቀጥል የቅዱስ ሲኖዶስ #የቅዱስ ሲኖዶስ ልዕልናና ሕልውና በተመለከተ ፣ #የ43ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ሪፖርት እንዲሁም #ሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት በሚሉ አጀንዳዎች ላይ ውይይት እንደሚያደርግ ይጠበቃል ብለዋል።