ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙 @satenawmedia1 Channel on Telegram

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

@satenawmedia1


ትክክለኛ ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ, ያልተነገረውን እንነግርዎታለን‼️



Ethiopia | Ethiopianews | Addismereja

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media (Amharic)

ሳተናው ሚዲያ በኢትዮጵያ የሚገኘው አሁኑን በውስጣዊ መረጃ ዘመን የሚባሉ ኢትዮጵያዊያንን በመብት ተስፋ ለሚቀበል፣ በኢትዮጵያ ከተማ ለሚያጋድሩ፣ ብሄራዊ አጀንዳችንን በማፍራት መረጃ ያድርጉና ዘምታ የሚጠቅም ነው። አሁንም የደረሰውን መነሻ የዚህ እዚህ ቻነል ሊኖር መሆኑን እና መረጃ ለመረጃ ይጠቀሙ። የሳተናው ሚዲያ ሰነድ የሆነው፣ የአዛዦ የቴሌግራም ድርጅት ነው፣ እና አዳዲᝪ ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ለመድረስ ይለጣል።

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 16:14


https://vm.tiktok.com/ZMkppjHeY/

每天点击我的视频,中文进步更快! (Měitiān diǎnjī wǒ de shìpín, Zhōngwén jìnbù gèng kuài!)

"Click on our videos every day to improve your Chinese step by step!"

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 15:47


#CapitalNews የአይኤምኤፍ ዋና ዳይሬክተር ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል

የአለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ዋና ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ ዛሬ እና ነገ የካቲት 2፤ 2017 ዓ.ም ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት የሚያደርጉ ሲሆን   እ.ኤ.አ ዋና ዳይሬክተሯ በ2019 የተቋሙ ኃላፊ ከሆኑ በኋላ በኢትዮጵያ የስራ ጉብኝት ሲያደርጉ ይህ የመጀመሪያቸው መሆኑ ተነግሯል ።

ክሪስታሊና ጆርጂዬቫ በጉብኝታቸው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ከከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እድገት እንዲሁም ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፖሊሲዎች እና በኢኮኖሚ ማሻሻያዎች ዙሪያ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል ተብሏል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 15:45


የኢሳያስ አፈወርቂ ተቃዋሚዎች

'ብርጌድ ንሐመዱ' የተሰኘዉ የፕሬዝዳንት ኢሳያስ አገዛዝ ተቃዋሚ ቡድን አዲስአበባ ላይ ቢሮ ሊከፍት ነዉ ተባለ
‼️

👉ቡድኑ ከሁለት ሳምንት በፊት ቦሌ አካባቢ ስብስብ ማካሄዱ ይታወሳል።
በውጭ አገራት የተመሠረተው 'ብርጌድ ንሐመዱ' የተሠኘው የኤርትራ ተቃዋሚዎች ስብስብ ኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣዮቹ ጥቂት ቀናት ቢሮ ሊከፍት መኾኑን መስማቱን አፍሪካ ኢንተለጀንስ ዘግቧል።
ቡድኑ ከሳምንት በፊት በአዲስ አበባ ባደረገው ስብሰባ ላይ ከተለያዩ የዓለም ክፍሎች የተወከሉ የንቅናቄው አባላት እንደተሳተፉ በወቅቱ ተዘግቦ ነበር።
ንቅናቄው በውጭ አገር የተመሠረተው ከኹለት ዓመት በፊት ሲኾን፣ በተለያዩ የምዕራቡ ዓለም አገራት የኤርትራ ኢምባሲዎችና የመንግሥት ደጋፊዎች ያካሄዷቸውን የባሕል ፌስቲቫሎች በማወክና በማስተጓጎል ይታወቃል።
#ዋዜማ

የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 14:38


የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ከደህንነት መረጃ ታገዱ ‼️

አሜሪካንን በፕሬዝዳንትነት ያገለገሉ መሪዎች በየዕለቱ ያሉ የአሜሪካ ደህንነት መረጃዎች እንዲያውቁት የሚፈቅድ ህግ አላት፡፡

ከአራት ዓመት በፊት በስልጣን ላይ የነበሩት ዶናልድ ትራምፕ በምርጫ ተሸንፈው ስልጣን ለጆ ባይደን ካስረከቡ በኋላ ይህ አሰራር ከዶናልድ ትራምፕ ላይ ተሸሮ ነበር፡፡

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በወቅቱ ዶናልድ ትራምፕ የሚታመኑ ሰዉ ባለመሆናቸው የአሜሪካ ዕለታዊ ደህንነት መረጃ ሊደርሳቸው አይገባም ሲሉ አግደዋቸው ነበር፡፡

በዳግም ምርጫ ድል ወደ ነጩ ቤተ መንግስት የተመለሱት ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በተራቸው ጆ ባይደን የአሜሪካ ዕለታዊ የደህንነት መረጃ ሊደርሰው አይገባም ሲሉ አግደዋቸዋል፡፡

“ጆ ተባረሃል፣ አንተ የአሜሪካ ሚስጢራዊ መረጃ ሊደርስህ የሚገባ ሰው አይደለህም” ሲሉ ትሩዝ ሶሻል በተሰኘው የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ጽፈዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ከ ባይደን በተጨማሪም የቀድሞ የሀገሪቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ፣ የደህንነት አማካሪ ጆ ቦልተን እና ሌሎች ባለስልጣትንም አግደዋል፡፡(via Alain)
======================
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️
https://t.me/satenawmedia1

ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️

https://youtu.be/eCUtrzd8hu0

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 07:36


ዶናልድ ትራምፕ የአፍሪካ መሪዎች ሰው መሆናቸውን እጠራጠራለሁ አሉ‼️

👉🏿 ከ50 ዓመታት የአህጉሪቷ የነጻነት ጉዞ በኋላ፣ ለህዝባችው አስፈላጊውን መሠረተ ልማት ካላሟላችው ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?


👉🏿በወርቅ፣ በአልማዝ፣ በነዳጅ፣ በዩራኒየም፣ በብረት፣ በማዕድን፣ በብር፣ በማግኒዥየም፣ በነሐስ፣ በጋዝ የተፈጥሮ ሃብቶቻችው ላይ ተቀምጣችው፣ ህዝባችው በረሃብ፣ በትምህርት አለመዳረስ፣ በጤና አገልግሎት እጦት፣ ቢሞት፣ ሰው ነን ብላችው ታምናላችው?

👉🏿በስልጣን ላይ ቆይታችው፣የራሳችሁን  ዜጎች ለመግደል ከውጭ የጦር መሣሪያዎችን ስታስገቡ፣ ሰው ነን ብላችው ታስባላችው?

👉🏿የገዛ ዜጎቻችሁን እንደውሻ ስታንገላቱና ስትገድሉ፣ ማን ዜጎቻችሁን እንዲያከብር  ትጠብቃላችው?

👉🏿በራሳችው  አገር ላይ ቀማኛና ሌባ በመሆናችው ፣ የሃገራችሁን  ሀብቶች ሁሉ በመስረቅ፣ አብዛኞቹ ዜጋዎቻችው በስደትና በድህነት ውስጥ እንዲያልፉ ስታረጉ፣ የሰው ልጆ ነን ብላችው ታስባላችው?
ትራምፕ ይሄን የተናገሩት ሰሞኑን በዋሽንግተን ዋይት ሀውስ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ መሆኑን ተመልክቻለሁ።

የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 03:38


ኔታንያሁ በነጩ ቤተ መንግስት ‼️
#USA
#Israel ‼️

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ተገናኙ፡፡

ሁለቱ መሪዎች በነጩ ቤተ መንግስት ሲገናኙ ፍልስጤማውያን(የጋዛ ነዋሪዎች) ወደ ዮርዳኖስና ግብጽ መዛወር እንዳለባቸው ትራምፕ ደግመው ተናግረዋል፡፡

"እነሱ የሚሉት አንቀበልም ነው፥እኔምለው ግን ያረጉታል ነው "በሚል ልመና አይሉት ማስፈራሪያ ሀሳባቸውን አጽንዖት ሰተውበታል፡፡

ሌሎች አገራትም ይቀበሉታል የሚል እምነት አላቸው ትራምፕ፡፡

በፈራረሰው ጋዛ መኖር አይቻልም የሚሉት ትራምፕ ሀሳባቸው በበርካቶች ዘንድ ትችት እየተሰነዘረበት ነው፡፡

ወደ ሌላ ቦታ መወሰድ አለባቸው፡ በወደመው ህንጻ ምን ይሰራሉ ባይ ናቸው፡፡

ለበርካታ አስርት ዓመታት የሞት ምድር ከሆነው ጋእ ሰዎች ተዛውረው በደስታ ይኖራሉ ያሉ ሲሆን በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ከፍተኛ ትችት እያስተናገዱም ነው፡፡

ኔታንያሁም በጋዛ ያስቀመጧቸውን ሶስት ግቦች አንድ በአንድ ማስፈጸማቸውን እንደሚቀጥሉ ለጋዜጠኞች መግለጻቸውም ስጋቱን የከፋ ያደርገዋል፡፡

ዘገባው የሲ ኤን ኤን እና አልጀዚራ ነው፡፡

===========================
ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇
https://t.me/satenawmedia1

YouTube :https://youtu.be/eCUtrzd8hu0

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 03:23


https://youtu.be/eCUtrzd8hu0

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 03:19


በኮሪደር ልማት የተሳተፉ ከ400 በላይ ኮንትራክተሮች መንግስት ክፍያ ሊፈፅምላቸው እንዳልቻለ ተናገሩ

(መሠረት ሚድያ)- በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ካዛንችስ ካሉ ቦታዎች ለተነሱ ሰዎች በፍጥነት የተዘጋጁ የጋራ መኖርያ ቤቶችን ያዘጋጁ ከ400 በላይ ኮንትራክተሮች ክፍያቸውን መንግስት እንደያዘባቸው ገልፀው ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንዳሉ ተናገሩ።

ኮንትራክተሮቹ ለመሠረት ሚድያ በሰጡት መረጃ መሰረት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ኮንትራክተሮቹ በግዴታ ከ3 ሺህ በላይ ቤቶችን ለኮሪደር ተነሺዎች እንዲገነቡ ካደረገ በኋላ ክፍያ መፈፀም አልቻለም።

"በጥቃቅን እና አነስተኛ የተደራጀን እኛ ኮንትራክተሮች ከ3 ሺህ በላይ የ40/60 የጋራ መኖርያዎች ውስጥ ያሉ ለንግድ ተብለው የተሰሩ ክፍሎችን ወደ መኖርያነት ቀይረን ገንብተን ብንጨርስም መንግስት ክፍያችንን ከልክሎናል" የሚሉት ኮንትራክተሮቹ አብዛኞቹ በብድር ወስደው ስራውን ቢሰሩም አሁን ትርፉ ቀርቶ ብድራቸውን ለመክፈል ተቸግረው እንዳሉ አብራርተዋል፣ አንዳንዶቹ ብድሩን ለመክፈል የግል ንብረታቸውን ለመሸጥ እየተገደዱ እንደሆነ ተናግረዋል። 

እነዚህ ለተነሺዎች በኮንትራክተሮቹ የተዘጋጁ  ቤቶች በአያት፣ አራብሳ፣ ቡልቡላ እና አስኮ እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል።

"ቤቶች ልማት እና ፋይናንስ ቢሮዎችን ስንጠይቃቸው ምላሻቸው ገንዘብ የለንም ነው፣ ታድያ ገንዘብ ከሌላቸው ለምን እኛን አሰሩን?" የሚል ጥያቄ የሚያነሱት እነዚህ አነስተኛ እና ጥቃቅን ኮንትራክተሮች አንዳንዶቹ ቤተሰባቸው ጭምር ችግር ላይ እንደወደቀ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ከኮንትራክተሮቹ ጋር መረጃ ይለዋወጥበት የነበረ የቴሌግራም ግሩፕን ስራው ካለቀ በኋላ ሰው መረጃ እንዳይቀያየርበት መቆለፉን ለማየት ችለናል።

የቤቶች ልማት ኮንትራክተሮቹን ወደ ስራ ሲያስገባ ምንም አይነት ቅድመ ክፍያ እንዳይጠይቁ አስፈርሞ እንደነበር መሠረት ሚድያ የተመለከተው አንድ ሰነድ ያሳያል።

"ወደን ሳይሆን በግዴታ ነው ካለ ቅድመ ክፍያ ተስማምተን የገባነው፣ እንደዛ ካልተስማማን ወደፊት ምንም ስራ ከተማ ውስጥ መስራት አትችሉም ተብለን ማስፈራርያ ተሰጥቶን ነበር" ያሉት ግለሰቦቹ አሁን ላይ ለሁሉም ስራ ሳይከፈል የተከማቸው ገንዘብ 4.4 ቢልዮን ብር ገደማ እንደሆነ ጠቁመዋል።

መሠረት ሚድያ በዚህ ዙርያ ባደረገው ተጨማሪ ከ3 ሚልዮን ብር እስከ 42 ሚልዮን ብር የተያዘባቸው ኮንትራክተሮች እንዳሉ የተረዳ ሲሆን ከነዚህ ኮንትራክተሮች ውጪም በኮሪደር ልማት ዙርያ የመንገድ ግንባታ የተሳተፉ አቅማቸው ከፍ ያለ ኮንትራክተሮችም ክፍያ ተነፍጓቸው እንደሚገኙ ለማወቅ ተችላል።

MeseretMedia

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

08 Feb, 03:17


45 ሺህ 370 ዓመት እስር የተፈረደበት ቱርካዊ ግለሰብ

በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገንዘብ በማጭበርበር የተከሰሰው የቱርክ የፋርም ባንክ መስራች መህመት አይዲን በ45 ሺህ 376 አመት ከ6 ወር እስራት ተቀጣ።

መህመት አይዲን ፋርም ባንክ በሚል በኦንላይን በመሰረተው ተቋም ስም ሰዎች በምናብ እንስሳትን እና ሰብሎችን እንዲገዙ በማድረግ ገንዘብ አጭበርብሯል ተብሏል።

“ቶሱንኩክ” በሚል ቅጽ ስሙ የሚታወቀው መሃመት አይዲን ፋርም ባንክ በሚል የማጭበርበሪያ ድርጅቱ በኩል ከ130 ሺህ ሰዎች ከ131 ቢሊየን የቱርክ ሊራ በላይ ገንዘብ ሰብስቧል ነው የተባለው።

አቃቤ ህግ መህመት አይዲን እና ወንድሙ ፋቲህ አይዲን ህገወጥ ድርጅት በማቋቋም እና በማስተዳደር፣ በማጭበርበር እና በህገወጥ የገንዘብ ዝውውር ወንጀል ከ75 ሺህ ዓመታት በላይ እስራት እንዲቀጡም ጠይቀው ነበር።

መህመት አይዲን ባሳለፍነው ሰኞ በዋለው ችሎች ላይ ፍርድ ቤት ቀርቦ የተከራከረ ሲሆን፤ “ማንንም ለማታለል አላሰብኩም፣ የማጭበርበር አላማ አልነበረኝም” ሲል ተናግሯል።

የቱርክ ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ክርክር ከተመለከተ በኋላ ብይን የሰጠ ሲሆን፤ በዚህም መህመት አይዲን እና ወንድሙ የሆነው ፋቲህ አይዲን እያንዳንዳቸው በ45 ሺህ 376 አመት ከ6 ወር እስራት እንዲቀጡ ወስኗል።

ከእስር በተጨማሪም የ496 ሚሊየን የቱርክ ሊራ የገንዘብ ቅጣትም ውሳኔም ያሳለፈ ሲሆን፤ ገንዘቡን በ24 ወራ ጊዝ ውስጥ እንዲከፍም ትእዛዝ ሰጥቷል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

07 Feb, 18:20


የጦሩ አዛዡ ተያዘ(In custody)‼️
ኬንያ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አዛዥን መያዟን ኬንያ ይፋ አደረገች፡፡ የኢትዮጵያ እና ኬንያ መንግስት ድንበር ላይ የጀመሩት ኦፕሬሽን የቀጠለ ሲሆን፤ የኬንያ ጸረ ሽብር ቢሮ ዛሬ ባወጣው መረጃ የአካባቢው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት መሪ የሆነውን ሳዳም ቡኬን ከግብረአበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር አውያለሁ ብሏል፡፡ መሪው ሳዳም ቡኬ በሰሜናዊ ኬንያ በመርሳቢት እና ኢሲዎላ አውራጃዎች የቡድኑ መሪ እንደሆነ የኬንያ ዜና ምንጮች ዘግበዋል፡፡
#አyu

የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

07 Feb, 18:05


አጋቾቹ ተይዘዋል::ህፃኑም ተገኝቷል

ከታገተ በኋላ "2 ሚሊዮን ብር ካላመጣችሁ ህጻኑን አንሠጣችሁም" የተባለው ህጻን ሙዘኪር አሚር ደቡብ ወሎ አቀስታ ከተማ ተገኝቷል።

በቀን 24/5/2017 ዓም ከጊምባ ከተማ አደባባይ አጠገብ ከቤተሠቦቹ ቤት ተሠርቆ የነበረው ህጻን ልጅ በአቀስታ ከተማ ህጻኑ ታግቶ ከነበረበት ቤት ተገኝቷል።

"2ሚሊዮን ብር ካላመጣችሁ ልጁን በህይዎት ማገኘት አትችሉም" በማለት እናቱን ያስፈራራ የነበሩት አጋቾች አስፋው ማርየና ሀይማኖት ባምላክ የተባሉ ግለሠቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ይገኛል።

አጋቾቹ ከወልድያና ጎንደር አካባቢ እንደመጡ ተናግረዋል።ህጻኑ የተገኘው ከጊምባ ከተማ ተወስዶ አቀስታ ከተማ ጎማጣ አካባቢ ባዶ ቤት ውስጥ ታግቶ ነው የተገኘው።
መረጃው የአቀስታ ኮሙኒኬሽን ነው።

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

07 Feb, 11:52


ከነገ ጀምሮ የሥራ ሰዓት ለውጥ ይደረጋል ‼️

በጋምቤላ ክልል በሙቀት መጨመር ሳቢያ የመንግስት የሥራ ሰዓት ከነገ የካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ወራት የሚቆይ የሥራ ሰዓት ለውጥ ይደረጋል ተብሏል።

በዚህ መሰረት:-

📌የመደበኛው የሥራ ሰዓት ከጠዋቱ 1፡00 እስከ 6 ፡30 የነበረው ከ1፡00 እስከ 5፡30 ይሆናል።

📌ከሰዓት በኋላ ከ9፡00 እስከ 11፡30 የነበረው ከ10፡00 እስከ 12፡30 እንዲሆን ተወስኗል።

📌የሥራ ሰዓት ለውጡ በማጃንግ ዞን የመንገሺና ጎደሬ ወረዳዎችን እንደማይጨምር መጠቆማቸውን የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

07 Feb, 08:49


ትራምፕ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC)  ላይ ማዕቀብ ጥለዋል።

📌ትራምፕ " በአሜሪካ እና የቅርብ አጋሯ እስራኤል ላይ ቅቡለነት እና መሠረት የሌለው ተግባር እየፈጸመ ነው " ሲሉ የከሰሱትን የዓለም አቀፉ የጦር የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ የጣሉበት ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ላይ ፈርመዋል።

📌ትራምፕ ICC ላይ የጣሉት ዕቀባ እና ቪዛን የሚያጠቃልል ነው።

📌አሜሪካ የዚህ ዓለም አቀፍ ተቋም አባል አይደለችም።
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join
https://t.me/satenawmedia1

ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️

https://youtu.be/WoyjwnbwpSk?si=f5jjVYXYC84Es9wY

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

02 Feb, 07:07


ገዥው ብልጽግና ፓርቲ በዚህ ሰዓት (2:56) የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ባይሰጠውም የፓርቲውን ፕሬዚደንትና ምክትል ፕሬዚዳንቶች ምርጫ በማካሄድ ላይ እንደሚገኝ ታውቋል።

ከዚህ በፊት በሚዲያ በቀጥታ ስርጭት ሽፋን ተሰጥቶት ነበር ምርጫ የተካሄደው።

የወቅቱ ፕሬዝደንት ጠ/ሚ አብይ በመድረኩ ላይ "አብይን የምትመርጡ" የምትል ቃል ተናግረው "ለራሳቸው ድምፅ ሲያሰጡ" በሚል ሂደቱ ብዙ ትችትን እንዲያስተናግዱ አድርጎ ነበር።
___
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

02 Feb, 05:21


#ዶክተሩ ተገደለ‼️
የጉበት ፣ የቆሽትና የሀሞት ከረጢት ከፍተኛ እስፔሻሊስት ሀኪም ፣ መምህር፣በባህር ዳር ዩኒቨርስቲ በጥበበጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ውስጥ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር እና ተመራማሪ የሆነው ዶ/ር አንዷለም ዳኜ በባህርዳር ጥበበ ጊዮን እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሲሰራ አምሽቶ ወደ ፈለገ ህይወት ሆ/ል ሌላ የሚሰራው ኬዝ ኑሮት እየሄደ ባለበት ሰአት ከምሽቱ 1:00 አካባቢ ማንነታቸው ያልታወቁ ሰዎች ከመኪናው አስወርደው ገድለውታል።
ዶ/ር አንዷለም ዳኜ 37 አመቱ ሲሆን በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ብሎም በአገራችን  አሉን ከምንላቸው በቁጥር ትንሽ የዘርፉ ሰብ ስፔሻሊስት ሐኪሞቻች ውስጥ አንዱ ነበሩ።
ነፍስ ይማር
ለቤተሰቦቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን እንመኛለን።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

02 Feb, 03:48


ምስራቅና ሰመረ ታስረዋል

📌ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በፖሊስ ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ ተብላ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተወስዳ እንደታሰረችና ትናንት ፍርድ ቤት ቀርባ የ7 ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንደተጠየቀባት ታውቋል።

📌በተመሳሳይ በቴሌቪዥንና በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያዎች በማህበራዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ በሚያቀርበው ሂስ የሚታወቀው ሰመረ ካሳዬ( ባሪያው) በዛሬው እለት በፖሊስ ተይዞ በአዲስአበባ ፖሊስ ኮሚሽን በተለምዶ ማዕከላዊ በሚባለው እስር ቤት ታስሮ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Feb, 18:28


አሳዛኝ ክስተት ‼️

ታዳጊዋ ተደፍራ ከተገድለች በሆላ ተሰቅላ ተገኝታለች ፡፡

ሲምቦ ብርሃኑ ትባላለች የ8 አመት ታዳጊ ስትሆን ነዋሪነቷ በምዕራብ ሸዋ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ ሲሆን የአስገድዶ መድፈር ወንጀል ከተፈፀመባት በኋላ ህይወቷ ሲያልፍ አስክሬ* ን ሰቅ* ው ሄዷል።

ለታዳጊዋ ሲምቦ ብርሃኑ ፍትህ
እየተጠየቀ ይገኛል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Feb, 16:47


https://vm.tiktok.com/ZMkVWpnQN/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Feb, 13:53


"ለምንድን ነው እርዳታው በመቋረጡ የምትንጫጩት?" ኡህሩ

አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ በኤክስ ገፃቸው እንደፃፉት!...
👇
<<የቀድሞው የኬንያ ፕረዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የአሜሪካ መንግሥት ለአገራቸው ሲሰጥ የነበረውን ዕርዳታ በማቆሙ ላዘኑ ኬንያውያን የሰጡትን አስተያየት አድምጬ አስተሳሰባቸውን በጣም አደነቅሁ:-

"ለምንድን ነው እርዳታው በመቋረጡ የምትንጫጩት? አሜሪካ አገራችሁ አይደለም፣ የናንተ መንግሥት አይደለም፣ የአሜሪካ መንግሥት ለናንተ ርዳታ የሚሰጥበት ምንም ምክንያት የለውም፣ ለአሜሪካ ግብር አትከፍሉም፥ ርዳታው ቀድሞውንም ምክንያታዊ አይደለም፣ ይህ የማንቂያ ደወል ሊሆነን ይገባል እንጂ ማለቃቀስ የለብንም፤ ስለዚህ ራሳችንን ለመርዳት ምን ማድረግ አለብን ብለን ራሳችንን መጠየቅ አለብን፤ ሐብታችንን በአግባቡ ለመጠቀም የምናስብበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፤ ሐብታችንን ለጠመንጃና ጥይት መግዣም አይደለም የምናውለው? ወንድም እህቶቹን፥ ወገኖቹን ለመግደል ለመገዳደል አይደለም የምንጠቀመው? ሐብታችንን ለጥፋት ዓላማ እያዋልን ገንዘብ ልመና ከሚንዞር፣ ሲናጣ ከሚንጫጫ ፀጋዎቻችንን ለተገቢው ዓላማ ማዋል አለብን" ነው ያሉት።

ኡሁሩ እውነታቸውን ነው ያሉት። ጉዳዩ እኛንም ይመለከታል፣ መልዕክቱ ለእኛም ጭምር ያገለግላል። እንዲያውም ከኬንያ በላይ የተረጂነት በሽታ ያጠቃው እኛን ነው። ሳናጣ ያጣን፣ እያለን የደሀየን እንቆቅልሽ የሆንን ሕዝቦች ነን። ባልሠለጠነ የፖለቲካ ባሕላችን ምክንያት የሚከሰቱ ልዩነቶች ለሚያስከትሉት ጦርነቶች የምናውለው ህልቆ መሳፍርት ሐብት፣ የምናባክናው ጊዜ፣ የሚጠፋው አምራች የሰው ሐይል በአግባቡ ብንጠቀምበት የትና የት ባደረሰን ነበር።
በሥርቆት የሚናባክነው ሲጨመርበት ደግሞ...። አፍሪካውያን በሙሉ የዚህ የተረጂነትና የአባካኝነት በሽታ ተጠቂዎች ቢሆኑም የእኛ የኢትዮጵያውያን ግን የከፋ ነው። ስለዚህ የኡሁሩን የማንቂያ መልዕክት በፍጥነት መጠቀም ይኖርብናል።>>
___
ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ለመከታተል የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Feb, 13:51


"ለባርነት ጨረታ" ቀርባ የነበረችው ኢትዮጵያዊት 700 ሺህ ብር ተከፍሎ ነጻ መውጣቷን ተናገረች‼️

ዓርብ ጥር 23 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሊቢያ "ለባርነት ጨረታ ቀርባ" የነበረችው ኢትዮጵያዊቷ ነሒማ ጀማል ለአጋቾቿ 700 ሺህ ብር ተከፍሎ ነጻ መውጣቷን ተናገረች።

በፎቶዎች እና በቪዲዮዎች ላይ አፏ በጨርቅ ተለጉሞ ስቃይ ሲደርስባት ትታይ የነበረችው ነሒማ በቤተሰቧ አማካይነት ገንዘብ ከኢትዮጵያ ተሰባስቦ ከተላከ በኋላ ከሁለት ቀናት በፊት አጋቾቿ ወደ ከተማ አምጥተው እንደለቀቋቸው አስረድታለች።

ታግታ ከነበረችበት ስፍራ እሷን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ቢኖሩም የተለቀቁት ገንዘብ የተከፈለላቸው "ውስን ሰዎች ነበሩ" ማለቷን ከቢቢሲ ጋር ባደረገችው ቆይታ ገልጻለች

እንዱሁም በአሁኑ ወቅት በሊቢያ እንደምትገኛና "ከዚህ በኋላ ምን እንደሚፈጠር አላውቅም" ስትል ጭንቀት ላይ እንደሆነች ተናግራለች።

ተማሪ የነበረችው ነሒማ ከኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ፣ በአዲስ አበባ በኩል ወደ በጎንደር በማምራት ከኢትዮጵያ በመውጣት ነበር ስራ አለ ተብላ ወደ ሊቢያ ያቀናችው

አዲስ አበባ የተዋወቃቻቸው ሁለት ኢትዮጵያውያን ወንዶች በሰሃራ በረሃ በውሃ ጥም ሕይወታቸው አልፏል ብላለች

ለሌሎች ስደትን አማራጭ ለሚያደርጉ "አገራቸው ውስጥ ቢቀመጡ ይሻላቸዋል፣ መንገድ ላይ በሽታ አለ፣ ሞት አለ፤ ብዙ ጓደኞቼ መንገድ ላይ ሞተዋል" ስትል መክራለች

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Feb, 12:18


https://vm.tiktok.com/ZMkVpBTE9/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Feb, 05:55


በአርትስ ቴሌቪዥን የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅነት የምናውቃት ምስራቅ ተረፈ "ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ? በሚል በፖሊስ የተወሰደች ሲሆን ፖሊስ የ7 ቀናት የምርመራ ጊዜ መጠየቁ ተሰማ‼️

ፖሊስ፣ ምሥራቅን አዲስ አበባ፣ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ችሎት እንዳቀረባት፣ ፍርድ ቤቱም ፖሊስ ያቀረበውን ጥያቄ በመቀበል፣ "ምርመራውን አጠናቆ እንዲያቀርባት" በሚል ለጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ መስጠቱን ተከትሎ፣ ምሥራቅ አሁን በአዲስ አበባ ፖሊስ እስር ላይ እንደምትገኝ ወዳጆቿ ገልጸዋል።

የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Feb, 04:27


የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት “ሕዝብን ሲያማርሩና ሲያንገላቱ ለነበሩ ተቋማት ሽልማት ሰጥቷል ከተባልኩኝ ሀላፊነቱን እወስዳለሁ” ሲል ተናገረ፡፡

ድርጅቱ ተቋማቱን ሲያወዳድር የውድድር ሒደቱ ከሙስናና ከብልሹ አሰራር የፀዳ ነውም ብሏል፡፡በኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት በኩል ከዚህ ቀደም ሽልማት ያገኘ ድርጅት በምርቶች ላይ አላግባብ ዋጋ በመጨመሩ እንዲዘጋ መደረጉንም ተሰምቷል፡፡

የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴዎድሮስ መብራት አሁን ላይ ሽልማት የሚገዙና የሚሸጡ በስፋት እየታየ መሆኑ አንስተው በእነኚ ሽልማት ሰጪ አካላት ምክንያት ሕዝብን የሚያንገላቱና የሚያማርሩ ተቋማት ሳይቀር ተሸላሚ እየሆኑ ነው ብለዋል፡፡

አያይዘውም የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ግን ለትርፍ የተቋቋመ ባለመሆኑ ከውድድር ሒደቱ ጀምሮ ያሉ ሒደቶች ከሙስና የፀዱ ናቸው፤ ሽልማት የሚያገኙ ተቋማትም በትክክል መስፈርቱን የሚያሟሉ መሆናቸውን እናረጋግጣለን ሲሉ ስራ አስፈፃሚው ተናግረዋል፡፡

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Jan, 18:44


#መረጃ ‼️

በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመሩ ናቸዉ የተባሉ የታጠቁ ግለሰቦች በዛሬው እለት መቐለ ኤፍኤም 104.4 ሬድዮን ለመቆጣጠር ሙከራ አርገው ነበር ተባለ ‼️

በትግራይ ክልል ባለስልጣናት መሀል እየተካረረ የመጣውን ውዝግብ ተከትሎ በዛሬው እለት የታጠቁ ግለሰቦች የመቐለ ኤፍኤም 104.4 ሬድዮን ለመቆጣጠር ሙከራ አርገው እንደነበር ዳጉ ጆርናል ከመሠረት ሚዲያ ዘገባ ተመልክቷል።

ሙከራው የተካሄደው በዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በሚመራው ቡድን አባላት መሆኑን ምንጮቼ ነግረዉኛል ያለዉ ሚዲያዉ ሙከራው ግን ያልተሳካ ነበር ሲል ዘግቧል።

"ታጣቂዎቹን ወደ ሬድዮ ጣቢያው ይዞ የገባው በእነ ዶ/ር ደብረፅዮን የተሾመ ዘመንፈስ ቅዱስ ፍስሃ የተባለ ግለሰብ ነው" ያሉት ምንጫችን ድርጊቱ ሲከሽፍ የኤፍኤም ሬድዮ ጣቢያውን ማህተም ይዘው ሲወጡ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቁመዋል።

ምን ያህል ታጣቂዎች ወደ ሬድዮ ጣብያው እንደገቡ እንዲሁም አላማቸው ምን እንደነበር እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም።
(meseret media)

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Jan, 10:26


https://youtu.be/sswJposy2RQ

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Jan, 10:23


#USA ‼️

አዲሱ የትራንፕ አስተዳደር የግብረ ሰዶማዊያን ምልክት የሆነውን ማንዲራ እንዲሁም "black lives matter" በየትኛውም የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ በህንፃዎች እና በፌደራል ተቋማት ላይ እንዳይሰቀል ከልክለዋል‼️
በተጨማሪም ይህንን መመሪያ የጣሱ የመንግስት ሰራተኞች ከስራ መባረርን ጨምሮ የዲሲፕሊን እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ትእዛዝ ሰጥተዋል።
አዩ
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Jan, 10:10


#ህጻናት በአፍመፍቻ ቋንቋቸው እንዲማሩ የሚያደርገውና የአማርኛ ቋንቋ የትምህርት አይነትን ከትምህርት ስርዓት የሚያስወጣ የአጠቃላይ የትምህርት አዋጅ ጸደቀ

የሀገሪቱ ህጎች ሁሉ የበላይ ነው የሚባለው ህገ መንግስቱን ይቃረናል የሚል የሰላ ትችት የቀረበበት የአጠቃላይ የትምህርት አዋጅን የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አፅድቆታል፡፡

ምክር ቤቱ ያጸደቀው አጠቃላይ የትምህርት አዋጅ የምክር ቤት አባላት ህገ መንግስቱን ይቃረናል ሲሉ ተችተውታል፡፡

የምክር ቤቱ አባል ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) አዋጁ የአንድ መግባቢያ የሀገራዊን ቋንቋ አስፈላጊነት የዘነጋን ይመስለኛል ብለዋል፡፡

ህፃናትን በአፍ መፍቻቸው ቋንቋ ማስተማር መሰረታዊ የህፃናት መብት መሆኑን የጠቆሙት ዶ/ር ደሳለኝ ህፃናት በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው የማስተማር አስፈላጊነት ያክል ደግሞ አንድ አስተሳሳሪ የሆነ ሀገራዊ ቋንቋ አስፈላጊነት መርሳት የለብንም ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የ 1986 የትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ አማርኛ ቋንቋ በመላ ሀገሪቱ ትምህርት ቤቶች እንደ አንድ የትምህርት አይነት መስጠትን ይፈቅድ ነበር፡፡

ባለፈው ዓመት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፀደቀው አዲሱ የትምህርት እና ስልጠና ፖሊሲ ግን ይህንን ጉዳይ እንዲለወጥ ማድረጉን ጠቅሰዋል፡፡

እንደ እኔ አማርኛ ቋንቋ ኢትዮጵያ በረጅም ጊዜ በነበረችው የታሪክ መስተጋብር ውስጥ በጥሩ እና በመጥፎ የታሪክ ዘመናቸው ውስጥ አነሰም በዛም መስተጋብር ማስተሳሰሪያ ሆኖ ያገለገለ ቋንቋ ነው ብለዋል፡፡

የሰሜኑ ከደቡቡ የምስራቁ ከምዕራቡ ከራሱ ቋንቋ በተጨማሪ ሚግባባት ቋንቋ አማርኛ ነው፡፡ ይህን ቋንቋ በተለይ ከ1960ዎቹ እንቅስቃሴ ጀምሮ ቋንቋውን የአንድ ህዝብ ብቻ አድርጎ በኢትዮጵያዊያን መካከል ያለውን ድልድይ ፈጣሪ ቋንቋ የማሳነስ ሁኔታ እስከ ዛሬ ድረስ ይስተዋላል ብለዋል፡፡

‘’እኔ አማራ ስለሆንኩ አይደለም ይህን ጥያቄ የማነሳው’’ ያሉት ደሳለኝ ቢያንስ ልጆቻችን የሚነጋገሩበት ሚግባቡበት ቢጣሉ የሚታረቁበት አንድ የጋራ ቋንቋ ቢኖራቸው ለዚህም አማርኛ ቢያንስ ከ3ኛ ክፍል ጀምሮ በመደበኛ አስከ 12 ክፍል ድረስ እንደ አንድ የትምህርት አይነት እንዲሰጥ በአዋጁ ቢካተት ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ለጥያቄዎቹ ምላሽ የሰጡት በምክር ቤቱ የሰው ሃብት ቴክኖሎጂ ስራ ስምሪት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ስብሳቢ የሆኑት ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር)አንድ ሀገራዊ ቋንቋ ቢሰጥ ለሚለው የትኛው ነው አገራዊ ቋንቋ? እስከዛሬ ድረስ በቋሚ ኮሚቴም ስንወያይበት ይሄ ነው ተብሎ አልተነገረንም ብለዋል፡፡

እኔም የትኛው ነው? አገራዊ ቋንቋ የሚለውን ጥያቄ ሳነሳ ነበር ዛሬ ግን ያነሱት የምክር ቤት አባል አማረኛ ቋንቋ ነው ብለዋል በግልጽ የተቀመጠው ግን አማርኛ ቋንቋ የፌደራል የስራ ቋንቋ እንደሆነ ነው ብለዋል፡፡

ሌላው አቶ ጋሻነው ዳኛው የተባሉ የምክር ቤቱ አባል የትኛውም ህግ የሚመነጨው ከህገ - መንግስቱ መሆን አለበት ይላሉ፡፡ አሁን የወጣው አዋጅ ግን ህገመንግስቱ እስኪሻሻል ይላል፤ እስኪሻሻል ብሎ ህግ ማውጣት ይቻላል ወይ የሚል ጥያቄን ጠይቀዋል፡፡

ሌላው አዋጁ ከህገ መንግስቱ ጋር ይጣረሳል የሚለው ጥያቄ ያነሱት የምክር ቤቱ አባል  አበባው ደሳለው(ዶ/ር) ናቸው፡፡

ዶ/ር አበባው የኢትዮጵያ የስራ ቋንቋ አማርኛ ነው ይላል ህገመንግስቱ ደግሞ አንድ ህግ ሲወጣ ከህገ መንግስት ጋር ከተጣረሰ ተፈፃሚነት አይኖረውም ይላል ለምን የማይፈጸም ህግ እናወጣለን ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

አዋጆች ሲወጡ የህብረተሰቡን ችግሮች ለመፍታት ነው ችግር የማይፈታ ነገር በአዋጁ ላይ ለምንድነው ለማስቀመጥ የተገደዳችሁት ሲሉ ዶክተር አበባ ጠይቀዋል፡፡ 

ነገሪ ሌንጮ(ዶ/ር) አዋጁ ከህገመንግስቱ ጋር የሚጣረስ ነገር የለውም ብለዋል፡፡

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

11 Jan, 17:01


https://vm.tiktok.com/ZMk5yGkMD/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

11 Jan, 16:50


ከፍተኛ የመሬት መንቀጥቀጥ‼️
ከደቂቃዎች በፊት 12:19 ደቂቃ ላይ በአዋሽ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 5.2 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ‼️
ንዝረቱ በአዋሽ፣በአዲስ አበባ እንዲሁም በደብረብርሃን ከፍተኛ እንደነበር ተጠቁሙዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

11 Jan, 14:49


🟢የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው፡፡

👉ሀሰን ሼክ ባለፈው አመት የካቲት ወር በ37ኛው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ከተሳተፉ ወዲህ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው
****
የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀመድ በዛሬው ዕለት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚያቀኑ ተገለጸ፡፡

ፕሬዝዳንቱ ወደ አዲስ አበባ የሚያቀኑት የሁለትዮሽ እና ቀጠናዊ ግንኙነትን በሚያጠናክሩ ጉዳዮች ላይ ለመምከር መሆኑ ተሰምቷል፡፡

ፕሬዝዳንት መሀመድ እና ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ የአንካራ ስምምነትን ተግባራዊ በማድረግ እና በሶማሊያ አዲሱ የሰላም ማስከበር ተልዕኮ ላይ የኢትዮጵያን ሚና ጨምሮ በተለያዩ ወሳኝ ጉዳዮች ላይ አተኩረው ይወያያሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሁለቱም መሪዎች በቀጠናዊ መረጋጋት፣ በኢኮኖሚ ትብብር እና በስትራቴጂያዊ አሰላለፍ ላይ ያላቸውን ትብብር ማሳደግ ይፈልጋሉ።

ይህ ጉብኝት ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ እ.ኤ.አ የካቲት 17 ቀን 2023 በ37ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ ላይ ከተሳተፉበት ጊዜ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚደረግ ነው፡፡

በወቅቱ ሀገራቱ ከነበሩበት ውጥረት ጋር በተያያዘ፤ የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይሎች የፕሬዝዳንቱን እንቅስቃሴ ለመገደብ ሞክረው ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት ጋር ተቀላቅለው ከሆቴላቸው እንዲወጡ ተገደዋል የሚል ውንጀላ የተሰማበት ነበር፡፡

ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሊላንድ ለንግድ እና ጦር ሰፈር የሚያገለግል ወደብ ለመከራየት ባለፈው አመት ጥር ወር የመግባብያ ስምምነት መፈጸሟን ተከትሎ ሞቃዲሾ እና አዲስአበባ ከአንድ አመት በላይ በውጥረት ውስጥ እንደቆዩ ይታወሳል፡፡

በቱርክ አደራዳሪነት ሁለቱን ሀገራት ለማሸማገል ሲደረግ የነበረው ጥረት ፍሬ አፍርቶ በታህሳስ 2024 የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በአንካራ ፊትለፊት ተገናኝተው ውጥረቶችን ለማቃለል ተስማተዋል፡፡

ስምምነቱ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከሶማሊያ የሉዓላዊነት ስጋቶች ጋር በማጣጣም አዲስ አበባ የሶማሊያ ወደቦችን እንድትጠቀም እንደሚያስችል መነገሩ ይታወሳል፡፡

በዲፕሎማሲ ውጥረት ውስጥ የቆዩት ሁለቱ ጎረቤት ሀገራት ከአንካራው የመሪዎች ስምምነት በኋላ ወደ አዲስአበባ እና ሞቃዲሾ ከፍተኛ ልዑካን ቡድናቸውን ልከው ተወያይተዋል
የፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ የዛሬው ጉብኝት የሁለትዮሽ ግንኙነቶችን ለማጠናከር እና ያልተፈቱ ጉዳዮችን መፍታት ላይ ያተኮረ መሆኑን የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ላይ አመላክቷል፡፡

በዛሬው ዕለት የሀገራቱ መሪዎች የሚያደርጉት ውይይት ውጤት የሶማሊያ እና ኢትዮጵያን የወደፊት ግንኙነት የሚቀርፅ እና ለቀጠናው ሰላም እና ልማት ሰፋ ያለ አንድምታ እንደሚኖረው ተዘግቧል፡፡
via alain

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

11 Jan, 11:09


https://youtube.com/shorts/BuubJAlDBp4?feature=share

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

11 Jan, 10:52


ወጋገን ባንክ የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ላይ በቀዳሚነት የተመዘገበ ኩባንያ ሆነ ‼️

ወጋገን ባንክ አክሲዮኑን በማስመዝገብ ወደ ገበያ ለማውጣት የሚያስችለውን ታሪካዊ እርምጃ መዉሰድ ችሏል።

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ አዲስ አበባ በሚገኘው የሳይንስ ሙዚየም ጥር 2 ቀን 2017 ዓ.ም ባዘጋጀው የተደራጀ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ይፋዊ የማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት ላይ ሲሆን በዚህም በገበያው ላይ በቀዳሚነት የተመዘገበ ኩባንያ መሆን መቻሉን አረጋግጧል።

ባንኩ በኢትዮጵያ በገበያው ላይ በመመዝገቡ ከተለምዷዊ የአክሲዮን መሸጫ ዘይቤዎች ወደ ዘመናዊ እና ቴክኖሎጂ ተኮር አማራጮች በመሸጋገር ተጨማሪ ካፒታል ለመሰብሰብ እንደሚያስችለዉ አስታውቋል።

Via Capital Newspaper

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

11 Jan, 06:30


#ዛሬ አዳሩን ከተከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጥ ከፍተኛው በሬክተር ስኬል 5.2 የተመዘገበ ሲሆን የተከሰተው ከለሊቱ 9:19 ከአዋሽ በስተሰሜን በ30ኪ.ሜ ርቀት ላይ ነው፣በዚህም አዲስ አበባን ጨምሮ ከፍተኛ የተባለ ንዝረት ተሰምቷል።
ዛሬ ለሊት የተከሰተ የመሬት መንቀጥቀጥ:-👇

1. ለሊት 8:42 በአፋር ገርባ ከአዋሽ ሰሜናዊ ምዕራብ በ12ኪ.ሜ ርቀት በሬክተር ስኬል 4.60 የሆነ

2. ለሊት 8:58 አማራ ክልል ብጨንቀኝ በሬክተር ስኬል 4.50 የሆነ

3. ለሊት 9:19 ከአዋሽ ባስተሰሜን በ30ኪ.ሜ ርቀት የምሽቱ ከፍተኛ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 5.20 የሆነ

4. ለሊት 10:50 ከመተኻራ በደቡባዊ ምስራቅ በ25ኪ.ሜ ርቀት በሬክተር ስኬል 4.30 የሆነ

5. አሁን ጧዋት 12:22 ከመተኻራ በደቡብ አቅጣጫ በ28ኪ.ሜ ርቀት በሬክተር ስኬል 4.40 የሆነ የመሬት መንቀጥቀጦች ተመዝግቧል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

11 Jan, 04:20


https://vm.tiktok.com/ZMk58hoHx/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Jan, 16:27


ኢትዮጵያ በ AUSSOM ተልዕኮ ሰራዊት እንድታዋጣ ሶማሊያ መወሰኗ ተሰማ‼️
የሶማሊያ መንግስት ኢትዮጵያ በ AUSSOM ተልዕኮ ሰራዊት እንድታዋጣ መወሰኑን የሶማሊያ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። ኢትዮጵያ የምታዋጣው የሰራዊት ቁጥር የሁለቱ ሃገራት መሪዎች ቀጣይ January 10, 2025 በዩጋንዳ በአካል ተገናኝተው እንደሚመክሩ ተዘግቧል።
#አዩ
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Jan, 12:23


ፋይዳ መታወቂያ ለባንኮች አስገዳጅ ኾነ‼️
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው ማስታወቂያ ከዛሬ ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም
ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ  ሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ  ወይም የፋይዳ ቁጥር ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሆኗል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Jan, 09:33


በመቐለ ከተማ አስተዳደር ቢሮ አከባቢ ሰላሚዊ ሰልፍ እየተካሄደ ይገኛል

በሰልፉ ላይ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የተሾሙት የመቐለ ከተማ ከንቲባ ስራቸዉን ይጀምሩ የሚል ጥያቄ ተነስቷል።

መቐለ ከተማ በጊዜያዊ አስተዳደሩና በነ ደብረፅዮን ቡዱን የተሾሙ ሁለት ከንቲባዎች እንዳሏት ይታወቃል።

በሰልፉ ላይ ከተማችን ለወራት ያለ ከንቲባ መቆየቷ አግባብነት የለውም፣ የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ውሳኔዎች ይከበሩ፣ የህዝባችንን አንድነት ለመሸርሸር የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች አጥብቀን እንቃወማለን፣ መንግስትን ለመገልበጥ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ይቁሙ፣ መቐለ የሰላምና ልማት ከተማ እንጂ የሁከትና ዓመፅ ከተማ አይደለችም የሚሉ ድምፆች በሰልፉ ላይ ተሰምተዋል።

በከፍተኛ የህወሓት አመራሮች መካከል በተፈጠረ ልዩነት በትግራይ ክልል ረዥም ጊዜ ያስቆጠሩ የመልካም አስተዳደደር፣ የሰላምና ፀጥታ ጥያቄዎች ሲነሱ የቆዩ ቢሆንም የክልል ፀጥታ ቢሮ በየተኛውም ቦታ የድጋፍም ሆነ የተቃዉሞ ሰልፎች እንዳይደረጉ ባስተለለፈው ውሳኔ መሰረት ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ሰልፎች ሳይካሄዱ ቆይተዋል።

ሰልፉ ዛሬ ታህሳስ 23 ማለዳ የጀመረ ሲሆን ወጣቶቹ ጥያቄያችን ሳይመለስ ከዚህ አንሄድም ሲሉም የተደመጡ ሲሆን ዳጉ ጆርናል ዝርዝር ጉዳዮችን ተከታትሎ የሚያደርሳቹ ይሆናል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Jan, 08:18


የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር በሠራተኞቹ እና በአምቡላንሶቹ ላይ በተፈፀመ ዘግናኝ ጥቃት እጅግ ማዘኑን ይገልፃል!
*
የማኅበሩ አምቡላንሶች በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ወለጋ ዞን ሲቡ ሲሬ ወረዳ እና በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ታች አርማጭሆ ወረዳ ለህይወት አድን ተግባር በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ባልታወቁ ኃይሎች በተተኮሰባቸው ጥይት የሁለቱም አምቡላንስ አሽከርካሪዎች ለከፍተኛ ጉዳት የተዳረጉ ሲሆን አምቡላንስ ተሽከርካሪዎቹም ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡

ማኅበሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ ሠራተኞቹን ጨምሮ በበጎፈቃደኞቹ እና ተሽከርካሪዎቹ ላይ በሚፈፀሙ ጥቃቶች አማካኝነት ሰብዓዊ አገልግሎቱን ለሚፈልጉ ወገኖች ለማድረስ ፈተና እየሆነበት ነው፡፡ በመሆኑም ጥቃት የሚፈፅሙ የትኛውም ተፋላሚ ኃይሎች ድርጊቱ ኢትዮጵያ የፈረመችውን ዓለም አቀፍ የጄኔቫ ሥምምነቶችን የሚፃረርና ከማኅበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ተረድተው የማኅበሩ ሠራተኞች፣ በጎፈቃደኞችም ሆኑ ተሽከርካሪዎች በነፃነት ተንቀሳቅሰው ሰብዓዊ ተግባራቸውን ማከናወን እንዲችሉ፣ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ፣ ከመሰል ድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ማኅበረሰቡም ድርጊቶቹን እንዲያወግዝ የተለመደ ተማፅኗችንን እናቀርባለን፡፡

በመጨረሻም ማኅበሩ የወገኖቻቸውን ህይወት ለመታደግ ሲንቀሳቀሱ የጥቃት ሰለባ በመሆን መተኪያ የሌላት ውድ ህይወታቸውን ላጡ ሠራተኞች እና በጎፈቃደኞች ቤተሰቦች መፅናናትን እንዲሁም ለተጎዱት በቶሎ ማገገምን ይመኝላቸዋል፡፡

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Jan, 06:35


‼️የቅድመ ጥንቃቄ መልዕክት‼️

🔥የእሳተ ገሞራ ከመከሰቱ በፊት መወሰድ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች

የእሳተ ገሞራ ፍንዳታ ከተፈጠረና በፍንዳታው ምክንያት ከሚከሰቱ አደጋዎች ሰዎችን ለማዳን ከመኖሪያቸው ማስወጣት አስፈላጊ ሆኖ በሚገኝበት ሁኔታ ቤት መልቀቅ ሊኖር ስለሚችል ከመንግስት አካላት የሚሰጡ ትዕዛዞችን እና መልዕክቶችን በትጋት መከታተል ይገባል።


ከሚመለከታቸው አካላት ከቤት ልቀቁ ከተባለ የሚከተሉትን እቃዎች ቀድመው ያዘጋጁ:-

👉🏽ደረቅ ምግቦችና የመጠጥ ውሃ
👉🏽ማስኮች
👉🏽አስፈላጊ መድሃኒቶች
👉🏽ፊት መሸፈኛ ሻርፖች
👉🏽 ሙሉ ሰውነትን የሚሸፍኑ ልብሶች
👉🏽 ስልክ መረጃ ለመለዋወጥ
👉🏽 የእጅ ባትሪዎች
👉🏽 የመጀመሪያ እርዳታ መሳሪያ ኪቶች
👉🏽 መነጽሮች
👉🏽 ሬድዮ
👉🏽 የጤና ባለሙያዎች ስልክ ቁጥር መያዝ

☝️የእሳተ ገሞራ ከተከሰተ በኋላ መደረግ  የሚገባቸው ጥንቃቄዎች

የእሳተ ገሞራው ጭስ የሚደርስበት አካባቢ ከሆኑ ጭሱ የተለያዩ ጎጂ ጋዞችን የያዘ በመሆኑ የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች ያድርጉ:-

🏡በቤት ውስጥ ከሆኑ 

👉🏽 ጭሱ እንዳይገባ መስኮቶችን እና በሮችን በመዝጋት ቤት ውስጥ መቀመጥ
👉🏽 የመጠጥ እና የቤት ውስጥ መገልገያ ውሃዎችን በደንብ መክደንእንስሳቶችም በጭሱ ምክንያት አደጋ ሊደርስባችው ስለሚችል በቤት ውስጥ በርና መስኮት ዘግቶ ማስቀመጥ
👉🏽ተዐማኒ ከሆኑ የመረጃ ሰጪ ተቋማት የሚሰጡ መረጃዎችን በንቃት መከታተል
👉🏽 የአየር ማቀዝቀዣ ፋኖችን ማጥፋት
👉🏽 በቤት ውስጥ ከሰል አለማቀጣጠል

🌆ከቤት ውጪ ከሆኑ

👉🏽 ወዳገኙት መጠለያ በመግባት መጠለል
👉🏽 በጋዙ ምክንያት የአይን፣ የአፍንጫ፣ የጉሮሮ ማቃጠል ካጋጠሞት ጭሱ ካለበት ቦታ ወደቤት በመግባት እራስዎን ያርቁ። ( ማቃጠሉ ካላቆመ ለህክምና ባለሙያ ደውለው ማሳወቅ)
👉🏽 የተቃጠለ አካል ካለ ወዲያውኑ አስፈላጊውን ህክምና ማድረግ
👉🏽 ቅልጥ አለቱ ሊፈስ ወደሚችልበት ቁልቁለታማ ወደ ሆኑ ቦታዎች አለመሄድ
👉🏽 ፊትን እና የተገለጠ የሰውነት ከፍሎችን መሸፈን፣ መነጽሮችንና የመተንፈሻ ማስኮችን ማድረግ
👉🏽 የመኪና ሞተር ማጥፋት
👉🏽 አቅመ ደካማ እና ህጻናትን መርዳት

ተከታዮቹን የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት የትስስር ገፆችን ይመልከቱ

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/GIE2023E
Telegram: - https://t.me/ethiopiangeology

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

01 Jan, 06:32


ትናንት ምሽት 4:17 ሰዓት ገደማ በሬክተር ስኬል 5.0 ሆኖ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በአፋር ክልል አዋሽ አካባቢ መከሰቱን ተከትሎ አዲስ አበባን ‼️ ጨምሮ፣በምንጃር፣በኮምቦልቻ፣በአዋሽ.... በተለያዩ አካባቢዎች ንዝረቱ መሰማቱ ተገልጿል።

በዚህም በርካታ የመዲናዋ ነዋሪዎች ከበድ ያለ ንዝረት እንደተሰማቸው ገልፀዋል። አንዳንዶቹም በፍርሃት ከቤታቸው የወጡም ነበሩ።

በኢትዮጵያ በትናትናው እለት ብቻ 6 ገደማ የመሬት መንቀጥቀጦች መመዝገባቸውን የአሜሪካ ጂኦሎጂካ ሰርቬይ መረጃ አመላክቷል።
ፎቶ:- ከአዲስ አበባ እንዲሁም በአፋር ክልል የመሬት መንቀጥቀጡ ያደረሰው ጉዳት

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Dec, 14:50


እስራኤል ሁቲ እንደ ሃማስ፣ ሂዝቦላህ ወይም የቀድሞ የሶርያ ፕሬዝዳንት ተመሳሳይ እጣ ፈንታ ይኖረዋል ስትል ዛተች ‼️

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእስራኤል አምባሳደር  በየመን በኢራን የሚደግፉት ሁቲዎች በእስራኤል ላይ የሚሳኤል ጥቃትን እንዲያቆሙ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጥታለች። ይህ ካልሆነ ደግሞ እንደ ሃማስ፣ ሂዝቦላህ እና የሶሪያው ባሻር አል-አሳድ ተመሳሳይ “አሳዛኝ እጣ ፈንታ” አደጋ ላይ ይጥለዋል ስትል እስራኤዝ ዝታለች።

በመንግስታቱ ድርጅት የእስራኤል አምባሳደሩ ዳኒ ዳኖን ኢራንንም አስጠንቅቀዋል። እስራኤል ኢራንን ጨምሮ በመካከለኛው ምስራቅ የትኛውንም ኢላማ የመምታት አቅም አላት ብለዋል። አክለውም እስራኤል የኢራን ተላላኪዎች የሚያደርሱትን ጥቃት እንደማትቀበል ገልፀዋል።

ዳኖን እስራኤል ተጨማሪ የሃውቲ ጥቃቶችን እንደማትቀበል ገልፀዋል። "ለሃውቲዎች፣ ምናልባት ባለፈው አመት በመካከለኛው ምስራቅ ላይ ስለ ደረሰው ነገር ትኩረት ስልትሰጡ ይሆናል"፤ ነገር ግን በሃማስ ላይ፣ በሂዝቦላህ፣ በአሳድ ላይ፣ እኛን ለማጥፋት ለሞከሩት ሁሉ የሆነውን ላስታውሳችሁ እፈልጋለሁ። ይህ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያህ ይሁን ብለዋል። ይህ ስጋት ለመፍጠር አይደለም ቃል ኪዳን ነው። ሃውቲም ተመሳሳይ አሳዛኝ እጣ ፈንታ ይኖረዋል ሲሉ ዳኖን ገልፀዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Dec, 09:21


አየር መንገዱ ከቻይናው ከጉዋንዡ ባዩን ዓለም አቀፍ አየር መንገድ እውቅና አገኘ ‼️

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከቻይናው ጉዋንዡ ባዩን ዓለም አቀፍ አየር መንገድ የቅርብ ትብብር ሽልማት ተበርክቶለታል።

እውቅናው የተሰጠው አየር መንገዱ ከጉዋንዡ ባዩን ጋር ባለው ጥብቅ የስራ ግንኙነት ሲሆን፤ የሁለቱን አየር መንገዶች ጠንካራ የስራ አጋርነት እንደሚያሳይም ተጠቅሷል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አሁን ላይ በጉዋንዡ ባዩን ዓለም አቀፍ አየር መንገድ በሳምንት 10 በረራዎችን እንደሚያደርግ አየር መንገዱ በማህበራዊ ትስስር ገፁ አመልክቷል። 

ለሁለቱ አየር መንገዶች የስራ ግንኙነት መጠናከር የጉዋንዡ ባዩን ዓለም አቀፍ አየር መንገድ ለሚያደርገው ቀጣይነት ያለው ድጋፍ አየር መንገዱ አመስግኖ በቀጣይም ትብብራቸውን ለማጠናከር እንደሚሰሩ ያለውን እምነት አስታውቋል

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Dec, 07:29


አስገዳጅ የሚሊሻ ስልጠና‼️
በአስገዳጅ የሚሊሻ ስልጠና ሳቢያ #በሰንዳፋ ከተማ ጠዋት ላይ ባጃጅ እና የፈረሰ ጋሪ እቅሰቃሴ መገደቡ ተገለጸ‼️
#በኦሮምያ ክልል ሰንዳፋ ከተማ የባጃጅ ሹፌሮች እና የፈረስ ጋሪ አስጋሪዎች በአስገዳጅ ሁኔታ የሚሊሻ ስለጠና እንዲወስዱ በመደረጉ የባጃጅ እና የፈረስ ጋሪ እንቅስቃሴ መገደቡ ተገለጸ፤ የከተማዋ ነዋሪዎች በትራንስፖረት እጥረት ችግር ላይ መውደቃቸውን አስታውቀዋል።

በግዳጅ እንዲወስዱ እየተደረገ ያለው የሚሊሻ ስልጠናው የተጀመረው ባሳለፍነው ሳምንት አርብ ታህሳስ 18 ቀን 2017 ዓ.ም መሆኑን እና እስከ ጥር ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቀጥል የተነገራቸው ሲሆን በስልጠናው ሳቢያ ከጠዋቱ 12 ሰዓት ተኩል እስከ 3 ሰዓት ተኩል ትራንስፖርት እንዲገደብ ማድረጉን አስታውቀዋል።

የሚልሻ ስልጠናውን መውሰድ ወደ ስራ ለመመለስ አስገዳጅ ቅድመ ሁኔታ መሆኑን የገለጸልን የባጃጅ አሽከርካሪ ስልጠናውን ያልወሰዱ የባጃጅ ሹፌሮች ፍቃድ እንደማያገኙ እንደተነገራቸው አስታውቋል።

በከተማዋ የፈረስ ጋሪ የሚያሽከረክሩም ስልጠናውን በግዳጅ እንዲወስዱ መደረጋቸውን አስታውቀዋል፤ “ስልጠናውን ካጠናቀቅን በኋላ በምሽት እና አስፈላጊ በሆነ ሰአት የከተማዋን ጸጥታ በማስጠበቅ ስራ ላይ እንደምንሰማራ ተነግሮናል” ብሏል።
#አዲስስታንዳርድ

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

31 Dec, 03:21


#update ‼️

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሴስሞሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊ ፕ/ር አታላይ አየለ ከሰሞኑ ህዝቡን እየረበሸ እና እያሳሰበ በሚገኘው የመሬት መንቀጥቀጥ ዙርያ ለቲክቫህ ሚድያ በሰጡት አስተያየት "መሬት በራሷ ጉዞ እየሄደች የምታስተነፍሰው ሃይል ነው ምንም የሚያስደንቅ ነገር አይደለም ቦታውም፣ በምን ያህል ርቀት ላይ እንደሆነ ይታወቃል በተለይ አዲስ አበባ ያለ ሰው ምንም ሊደነግጥ አይገባም" የሚል አስገራሚ ምላሽ ሰጥተው ተመለከትኩ


- የመሬት መንቀጥቀጡ በአዋሽ አካባቢ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እያፈናቀለ በሚገኝበት ወቅት

- በርካታ ህንፃዎች፣ የመኖርያ ቤቶች እና መንገድ ጭምር እየተሰነጣጠቀ ባለበት ግዜ፣ እንዲሁም

- ይህ ሁሉ የመሬት መንቀጥቀጥ በአንድ ቀን ውስጥ ብቻ እየተከሰተ ባለበት ሀገር ውስጥ በአደጋ ወቅት ሊደረጉ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች ይህ ነው የሚባል ስራ ባልተሰራበት ሁኔታ እንዲህ አይነት 'አታስቡ' እና 'አትደንግጡ' አይነት አስተያየት ፍፁም ተገቢ ያልሆነ እና ህዝብን ይበልጥ ለአደጋ ሊዳርግ የሚችል ሆኖ ተሰምቶኛል።

EliasMeseret

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

28 Dec, 08:27


ኢትዮጵያ ሳትካተት ቀረች‼️
ኢትዮጵያ በሶማሊያ በሚሰማራዉ በአዲሱ  የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ውስጥ ሳትካተት ቀረች‼️
በጸጥታው ምክር ቤት ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ ዉስጥ ለመካተት ያነሳችውን የተሳትፎ ጥያቄ ሶማልያ ሳትቀበለዉ ቀርታለች።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የፀጥታው ምክር ቤት በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት ድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ (AUSSOM) ለማቋቋም ትናንት አርብ ዕለት በውሳኔ ሃሳብ አጽድቋል።

15 አባላት ያሉት ምክር ቤት በእንግሊዝ መሪነት የቀረበውን ረቂቅ የውሳኔ ሃሳብ በ14 ድምጽ ሲያፀድቅ አሜሪካ የድምፅ ተአቅቦ አድርጋለች።

አምባሳደሩ  ኢትዮጵያ  የሚጠበቅባትን ለመወጣት ዝግጁ ናት ሲሉ ቢገልጹም ፤ የሶማልያው ተወካይ  በሰጡት ምላሽ ሶማልያ  የወታደሮቹን አሰፋፈር ብሔራዊ ጥቅሟን ባስከበረ መልኩ እንዲሆን መወሰኑን ገልጸዋል።

"አሁን ያለው የወታደሮች ድልድል  በስምምነት እንደሚጠናቀቅ አበክረን እንገልፃለን" ያሉት የሶማሊያ ተወካይ በአሁኑ ወቅት የግብፅን ጦር ጨምሮ 11,000 ወታደሮች ማሰባሰብ ችለናል ሲሉም ተናግረዋል።
  
https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

27 Dec, 15:54


🇸🇴 አል-ሸባብ በሶማሊያ የአየር ድብደባ መሪው መገደሉን ማረጋገጡ ተዘገበ

አክራሪው እስላማዊ ቡድን አል-ሸባብ* በጎርጎሮሳውያኑ 2022 በአሜሪካ በልዩ ሁኔታ በዓለም አቀፍ አሸባሪነት የተፈረጀው መሪው የሆነው መሀመድ ሚሬ በሶማሊያ መገደሉን ማረጋገጡን ጋሮዌ የቡድኑን መግለጫ በመጥቀስ ሐሙስ ዕለት ዘግቧል።

በሶማሊያ ደቡባዊ ክፍል በሚገኘው የታችኛው ሻቤሌ ክልል በአየር ጥቃት መገደሉን ጋሮዌ ዘግቧል። ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል ባይኖርም እንዲህ ዓይነቶቹ ጥቃቶች በአሜሪካና በሶማሊያ ጦር ኃይሎች በጋራ በተደጋጋሚ የሚካሄዱ መሆናቸውን ዘገባው አመልክቷል።

🔺አል-ሸባብ በሶማሊያ የሚገኝ እና ከአል-ቃይዳ* ጋር ግንኙነት ያለው የጂሃዲስት ታጣቂ ቡድን ነው። በሶማሊያ መንግስት ላይ የትጥቅ ተቃውሞ የሚያካሂድ ሲሆን በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ተልዕኮዎች ላይም እንቅፋት የሚፈጥር ቡድን ነው።

*አልቃይዳ እና አልሸባብ በሩሲያ እና በሌሎች በርካታ አገራት የታገዱ የሽብር ድርጅቶች ናቸው።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

27 Dec, 13:17


https://vm.tiktok.com/ZMkk9bxdn/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

27 Dec, 11:13


በሸገር ከተማ ለልማት በሚል ከ3 ሚሊየን ብር በላይ ሰብስበው ለግል ጥቅማቸው ያዋሉ አመራሮች በእስራት ተቀጡ‼️


በኦሮሚያ ክልል በሸገር ከተማ አስተዳደር ሱሉልታ ክፍለ ከተማ ለልማት በሚል ከማህበረሰቡ  ከሦስት ሚሊየን ብር በላይ በመሰብሰብ ለግል ጥቅማቸው በማዋላቸው በእስራት ሊቀጡ ችለዋል። 

በሸገር  ከተማ ቅርንጫፍ አቃቤ ህግ  አንደኛ ወንጀል ችሎት እንዳስታውቀው የወሠርቢ  ወረዳ አስተዳዳሪ ሲፊለቴ  ከበደ፣  የፋይናስ ፅ/ቤት ኃላፊ አሸብር ኦልጅራ፣ የማዘጋጃ ኃላፊ ጐታ ኤጀሪ፣ የወረዳው ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ገመቹ ማሞ የተባሉ አራት አመራሮች የሙስና ወንጀል ለመከላከል የወጣውን አዋጅ በመተላለፋቸው ክስ ተመስርቶባቸዋል።

ተከሳሾቹ ከሸገር ከተማ አስተዳደር እና ከክፍለ ከተማው ፍቃድ ሳይሰጣቸው  በሱሉልታ ከተማ ወሰርቢ ወረዳ ከተለያዩ ባለሀብቶች እና ከሌሎች ማህበረሰብ ክፍሎች  ለልማት በሚል በህገ ወጥ መንገድ በራሳቸው ስም በከፈቱት የባንክ ሂሳብ 3 ሚሊየን 80 ሺ ብር ሰብስበው ለግል ጥቅማቸው በማዋላቸው አቃቤ ህግ ክስ መስርቶባቸዋል።

በቀረበባቸው ክስ 2ተኛ እና 3ተኛ ተከሳሽ በቁጥጥር ስር ውለው የወንጀል ድርጊቱ አልፈፀምንም በማለት የእምነት ክህደት ቃላቸውን ሰጥተዋል።በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ በተከሰስኩበት ክስ ጥፋተኛ መሆናቸውን በማረጋገጥ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ተከሳሾችን በ5 አመት እስራት አና በ5 ሺ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ መወሰኑ የሸገር ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ ፍርድ ቤት አስታውቋል።በአንደኛ እና በአራተኛ ተከሳሾች ላይ ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱ ተገልጿል።
#dagujournal

የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

27 Dec, 09:46


4.9 በሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ በድጋሚ አጋጠመ

ዛሬ ሌሊቱንም በድጋሚ በሬክተር ስኬል 4.9 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ ተሰምቷል። 11 ሰዓት ገደማ ላይ የተሰማዉ ንዝረቱ እስካሁን ከታዩት የመሬት መንቀጥቀጦች ዘለግ ላሉ ሰከንዶች የቆየም እንደነበር ተሰምቷል።

የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ የመሬት መንቀጥቀጡ ከመተሃራ አቅጣጫ በስተሰሜን 26 ኪሜ ርቆ መሆኑን እና 4.9 በሬክተር ስኬል የተለካ መሆኑን አሳዉቋል።

በተከታታይ የተከሰተዉ የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.9 የተመዘገቡ ሲሆን በቀዳሚነት ከነበሩት ከፍ ያለ እና ሁነቱ አዲስ ሆኖ መታየት ከጀመረበት እና በወቅቱ ከታዩት የመሬት መንቀጥቀጥ ስሜቶች ጋር ተመሳሳይነት ያለዉ ነዉ።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

27 Dec, 05:32


አሐዱ ራዲዮና ቴሌቭዥን የፖለቲከኛው ጀዋር መሐመድ ቃለመጠይቅ ላለማስተላለፍ መወሰኑን የጣቢያው የቅርብ ምንጮች ገልፀዋል

አሐዱ ቃለመጠይቁን በኬንያ ናይሮቢ ተገኝቶ ከሰራ በኋላ እንደሚያስተላልፍም ማስታወቂያ ማስነገሩን አስታውሶ ሆኖም
አቶ ጀዋር ለቢቢሲ አማርኛ ተመሳሳይ ቃለመጠይቅ በመስጠቱ ምክንያት ለዚህ ውሳኔ እንዳበቃው ተጠቁሟል።

ከጣቢያው በጉዳዩ ላይ ይፋዊ ማብራሪያ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።

አቶ ጀዋር መሐመድ ከሰዓታት በፊት ምንጮችና ራዊ ድረገፁ ባሰፈረው ሐተታ ቃለመጠይቁ ሳይከለከል እንዳልቀረ በመጥቀስ ቃለመጠይቁን በአማራጭ ሚድያ ለመልቀቅ እንደሚገደድ ፅፏል።
Via_ankuar

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

26 Dec, 17:16


የጋሞ አባቶች በሰላም ዘርፍ ኢ/ር ቢጃይ ናይከር በኢኮኖሚ ዘርፍ ተሸለሙ

አንቴክስ ያዘጋጀው የመጀመሪያው የሰላም ዘርፍ እና የኢኮኖሚ ዘርፍ ሽልማት ዛሬ ታህሳስ 17/2017 ዓም በአፍሪካ ህብረት ተካሂዷል።

🏆 የሰላም ዘርፍ አሸናፊ የጋሞ አባቶች

🏆 የኢኮኖሚ ዘርፍ አሸናፊ ኢ/ር ቢጃይ ናይከር

ለሁለቱም አሸናፊዎች የ10 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተሰጥቷል።

ኢ/ር ቢጃይ ናይከር በተወካይ በኩል ሽልማቱን ከተቀበለ በኋላ ሽልማቱን ተጨማሪ 20 ሚሊዮን ብር በመጨመር ፌስቡክ ላይ ከዚህ በፊት እንደሚያደርገው እንደሚሸልም ገልጿል።

የBIW prize አላማውን በኢትዮጵያ ውስጥ ኢኮኖሚያዊ እድገትን ለማምጣት በተለየ መንገድ ጥረት ለሚያደርጉ እና በህዝቡ መካከል ሰላማዊ አብሮነትን ለማጎልበት ለሚተጉ በስራቸውም ለሌሎች አርአያ ለመሆን የቻሉ ግለሰቦችን እና ድርጅቶችን ማበረታታት እና ስራቸውንም ማገዝ ነው ።

አንቴክስ ጨርቃጨርቅ ኃ.የተ.የግ.ማ. በኦሮሚያ ክልል አዳማ ውስጥ የሚገኝ ሲሆን በአዳማ ኢንደስትርያል ፖርክ ከ10 በላይ ሼዶች ሲኖሩት ለ4500 ሰራተኞች የስራ እድል የፈጠረ ድርጅት ነው።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

26 Dec, 05:39


በአዲስ አበባ የቤት ሽያጭ ዋጋ ጭማሪ ባያሳይም ገዢ ያን ያህል የለም ። ለአዲስ ቤት ተከራዮች እየተጠራው ያለ የቤት ኪራይ ዋጋ አቅማቸውን ያገናዘበ አይደለም _ደላሎች ‼️

ፊደል ፖስት በአዲስ አበባ ከተማ ዞር ዞር በማለት “የቤት ግዢ እና ኪራይ ምን ይመስላል ?በማለት “ ደላሎችን ጠይቆ ነበር ።

የተገኘው መልስ በአጭሩ ይሄን ይመስላል ;

የቤት ግዢን በተመለከተ

መንግስት ኮሪደር ልማት ብሎ በሚጠራው ብዙ ቤት እየፈረሰ ስለሆነ ምድር ላይ ያለ ቤት ነገ ቢፈርስብኝስ በማለት ደፍሮ የመግዛት ነገር ብዙም የለም። የአፓርተመንት እና የኮንዶሚንየም ቤት በአንፃራዊነት ጭማሪ ባያሳይም ግዢ ያን ያክል አይደለም ። ሰው የመግዛት አቅሙ የተዳከመ ይመስላል ።ለቤት ብድር ከባንክ አለማግኘት የንግድ እንቀስቃሴ በአንዳንድ ዘርፎች ላይ መቀነስ ፣ የምግብ እና ሌሎች መሰረታዊ ነገሮች ዋጋ መጨመር ሰው ገነዘብ ቆጥቦ ወደ ቤት መግዣ እንዳያውለው ተፅእኖ አድርጓል።

ቤት ኪራይን በተመለከተ


ነባር ተከራዮች መንግስት ለሁለት አመት ከአከራዮች ጋር ስላዋዋላቸው አሁን የጨመረው የቤት ኪራይ ዋጋ አላገኛቸውም።

ነገር ግን ብዙ ቤት የፈረሰባቸው ሰዋች ለስራቸው አመቺ እንዲሆን ወይንም በምትኩ መንግስት የሰጣቸው ቤት ስለጠበባቸው ወደ ቤት መከራየት በመግባታቸው እንዲሁም በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች ያለውን ግጭት በመሸሸ ስራም ለመፈለግ ወደ ከተማዋ የሚፈልሰው ሰው ቁጥር የጨመረ ሲሆን ይሄም ለቤት ኪራይ ዋጋ መናር ጉልህ አስተዋፆ እያደረገ ይገኛል።

በተጨማሪም አከራዮች በሁለት አመት ውስጥ ዋጋ መጨመር ስለማይችሉ አዲስ ሰው ቤት ሲከራይ ያን ግምት ውስጥ በመክተት እስከ 50 ፐርሰንት ዋጋ ጭማሪ በማድረግ እያከራዩ ይገኛሉ ።

በአንፃራዊነት አነስተኛ ዋጋ ሲጠራባቸው የነበሩት በሸገር እና ጫፍ አዲስ አበባ ላይ ያሉ ቤቶች በአንድ አመት ውስጥ በአማካኝ እስከ ሰባ በመቶ የዋጋ ጭማሪ አሳይተዋል።

በመሀል ከተማ ያሉ አከራዮች በኑሮ መወደድ ምክንያት ኑሯቸውን ለመደጎም አዲስ ተከራይ ላይ ዋጋ የሚጨምሩ ሲሆን “በዚህ ዋጋ አከራየው አከራይው ።ቤት እየፈረሰ ስለሆነ ተከራይ በሽ ነው “በማለት ደላሎችም ለቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር ድርሻ አላቸው የሚሉ መልሶች ፊደል ፖስት በቃለ መጠይቁ አግኝቷል ።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

26 Dec, 04:42


አንጋፋው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በመንግስት መታገዱን ዋዜማ ሰምታለች። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ኢሰመጉን ያገደው፣ ከተቋቋመለት ዓላማ ውጭ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ያደርጋል በማለት ነው። የመንግሥት ጸጥታ ኃይሎች በአመራሮቹና ሠራተኞቹ ላይ ማስፈራሪያና ዛቻ እንደሚፈጽሙ ለበርካታ ወራት ሲገልጽ የቆየው ኢሰመጉ፣ ዋና ዳይሬክተሩ ዳን ይርጋ በዚኹ ዛቻና ማስፈራሪያ ሳቢያ ከአገር ለመሰደድ እንደተገደዱ በቅርቡ መግለጡ ይታወሳል። ባለሥልጣኑ በዲሞክራሲና መብቶች ዕድገት ማዕከል እና ጠበቆች ለሰብዓዊ መብቶች በተሰኙት ሲቪል ማኅበራት ላይ ባለፈው ኅዳር ወር በተመሳሳይ ምክንያት ጥሎት የነበረውን እገዳ ካነሳ በኋላ፣ ድርጅቶች የተሰጧቸውን የማስተካከያ ርምጃዎቾ ተግባራዊ አላደረጉም፤ ይልቁንም የቀድሞ ጥፋታቸውን ቀጥለውበታል በማለት በቅርቡ በድጋሚ እንዳገዳቸው አይዘነጋም።

[ዋዜማ]

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

26 Dec, 03:37


በ #ሆሳዕና ከተማ እንጀራ ላይ ባዕድ ነገር ቀላቅለው ለገበያ ሲያቀርቡ የተገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ‼️
በሀድያ ዞን በሆሳዕና ከተማ እንጀራ ላይ ጄሶ፣ ሳጋቱራ እና ሌሎች ነገሮችን ቀላቅለው ለገበያ ሲያቀርቡ የተገኙ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተገለጸ።
የሀድያ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ ተከተል ዶባሞ፤ እንደ ሆሳዕና ከተማ በ6ቱም ቀበሌያት ተሰውረው ህገ ወጥ ተግባር የሚሰሩ አካላት እንዳሉ በተደረገው ክትትል መድረስ እንደተቻለ ገልጸዋል።

እንደ አቶ ተከተል ማብራሪያ፤ የከተማና የዞኑ የንግድ ዘርፍ ከህግ አካላት ጋር በጋራ በመሆን በተደረገው ጥብቅ  ክትትል እንጀራን ከባዕድ ነገር ጋር ቀላቅለው ለገበያ ሲያቀርቡ የተገኙ 19 ቤቶች ሲታሸጉ 38 ሰዎች ደግሞ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ምንጮች ገልጸዋል።
#አዩ
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

06 Dec, 17:12


#RIP 🥹🥲🥲🥲🥲

የአንድ ወረዳ ሙሉ አመራሮች ተገደሉ‼️
በአማራ ክልል ከወደ ደጋዳሞት የተሰማው መረጃ አሳዛኝ ነው‼️ 
የአነደድ ወረዳ ኮሙኒኬሽን የደጋዳሞት ወረዳ አመራር የነበሩ 35 ሰዎች መገደላቸውን ከእነ ስም ዝርዝራቸው እንደሚከተለው አስቀምጧል።

1,ዋለ አለማየሁ...የወረዳው ዋ/አስተዳዳሪ
2,ቄ/እንዳለ ገበየሁ...ኮሚኒኬሽ ጽ/ቤት ኃላፊ
3,ዘመኑ ይባቤ...እንስሳት ሀብት ጽ/ቤት ኃላፊ
4,አይናለም ስንሻው...ውሃ ጽ/ቤት ኃላፊ
5,አንቢዛው ጠቅላይ...ትም/ጽ/ቤት ም/ኃላፊ
6,ወንድይፍራው ጌታነህ...አስ/ጽ/ቤት ኃላፊ
7,ጌታሰው ውቤ...ሲቭልሰርቪስ ጽ/ቤት ኃላፊ
8,ተመስገን መኮነን...ኢንቨስትመንት ጽ/ቤት ኃላፊ
9,ሞላ አንተነህ..ስፖርት ጽ/ቤት
10,ይፍረድ ወንድሜነህ...መንገድ ጽ/ቤት ኃላፊ
11,አስፋው ስንሻው...ገንዘብ ጽ/ቤት ኃላፊ
12,ጌታቸው የሽዋስ...ጤና ጽ/ቤት
13,  ተከታይ  ውድነህ   ገቢዎች ሀላፊ
14, ምግባሩ  አእምሮ መዘጋጃ  ምክትል
15,አይናለም ስንሻው   ውሀ  ጽ/ቤት ሀላፊ
16,ማስተዋል አሻግሬ አፈጉባኤ
17,ጎሹ  ወርቄ     መሬት ሀላፊ
18,ብናየው  ምስጋናው -ንግድ ሀላፊ
19, ከፋለ  ንብረት  መስኖና  ቆላማ ጽ/ቤት      
20, አበበ ይስማው  ማህበራት   ሀላፊ
21,ዘመኑ ሙሉነህ  ፖሊስ
22,አሰሜ  መኮነን  ምሊሻ
23,ምስጋናው   ምሊሻ
24,ይላቸው   ፈንታ  ምሊሻ 
25,አንሙት  አየነው  ምሊሻ ባለሙያ
26,የኔሰው  ምሊሻ 
27,ሽብሬ  አፈንጉስ  ግብርና ባለሙያ 
28,ማተቤ  ተመስገን  ገቢ ባለሙያ
29,በላይ ዋለ-ገቢዎች ቡድን መሪሌሎችም በስም ያልተጠቀሱ 6 አሉ ብሏል።
አሳዛኝ ነው

=====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇⬇️⬇️
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

06 Dec, 17:10


የዓለም ጤና ድርጅት ኃላፊ ቴድሮስ አድሃኖም በግጭት ወቅት የጤና ተቋማትን ማጥቃት መደበኛ ድርጊት እየሆነ ይገኛል ሲሉ ተናገሩ ‼️


ከጋዛ፣ ሊባኖስ እና ዩክሬን እስከ አፍጋኒስታን፣ ሄይቲ፣ ምያንማር እና ሱዳን ግጭቶች ድረስ የጤና ተቋማትን ማጥቃት አዲስ አሳሳቢ አዝማሚያ ሆኗል ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት ሃላፊ ቴዎድሮስ አድሃኖም ገብረእየሱስ ተናግረዋል።እ.ኤ.አ. በ2024 የዓለም ጤና ድርጅት በተለያዩ ሀገራት በጤና አጠባበቅ ተቋማት ላይ ከ1,200 በላይ ጥቃቶች መድረሳቸዉን አረጋግጠናል ሲሉ ቴድሮስ ተናግረዋል።

"ባለፉት ሶስት አመታት በጤና አጠባበቅ ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች ድግግሞሽ፣ መጠን እና ተፅእኖ መጨመር አይተናል" ብለዋል፡፡እ.ኤ.አ. በ2018 የአለም ጤና ድርጅት እንደዚህ አይነት ክስተቶችን መከታተል ከጀመረ በ21 ሀገራት እና ግዛቶች በጤና አጠባበቅ ላይ የተረጋገጡ ከ7,600 በላይ ጥቃቶች ሲደረጉ ከ2,600 በላይ የጤና ሰራተኞች እና ታማሚዎች ተገድለዋል፡፡5,400 ያህሉ ደግሞ ቆስለዋል።

ለእንደዚህ አይነት ጥቃቶች ተጠያቂነት ከሌለው እንደሚቀጥሉ ቴድሮስ አስጠንቅቀዋል።"ምርጡ መድሃኒት ሰላም ነው" ሲሉም አክለዋል፡፡ በጋዛ ሰርጥ የካማል አድዋን ሆስፒታል ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ የእስራኤል ወታደራዊ ተደጋጋሚ ጥቃቶች ገጥሞታል፤ ከነዚህም መካከል ሃሙስ እለት በደረሰበት ጥቃት አንድ የ16 አመት ልጅ በተሽከርካሪ ወንበር ላይ የተገደለ ሲሆን ቢያንስ 12 ሰዎች ቆስለዋል። እ.ኤ.አ በኖቬምበር 29፣ የእስራኤል ሰው አልባ አውሮፕላን የካማል አድዋን ሆስፒታል የፅኑ እንክብካቤ ክፍል ዳይሬክተር የሆኑትን ዶ/ር አህመድ አል ካህሎትን በተቋሙ መግቢያ በር በኩል እያለፉ ገድሏል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

06 Dec, 16:50


ከሰሞኑ የሰማነው የተወሰኑ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (መንግስት ኦነግ ሸኔ የሚለው) አባላት ሰላም መምረጥ ተስፋ ይሰጣል ‼️

አካሄዱ ላይ ግን ጥንቃቄ ካልተደረገበት ውጤቱ ከታሰበው በተቃራኒ እንዳይሆን ያሰጋል።

ዛሬ ጠዋት ስልኬን ስከፍት የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ልብስን የለበሱት ጃል ሰኚ ነጋሳ መግለጫ ሲሰጡ ተመለከትኩ። "በምን አግባብ?" የሚለው ትልቁ ጥያቄዬ ነበር፣ ምክንያቱም የሰራዊቱ አባል ያልሆነ ሰው ልብሱን ለብሶ ከተገኘ እንደ ከፍተኛ ወንጀል ስለሚቆጠር።

በርካቶች ይህን ሁኔታ አይተው "ቀድሞውም እኮ አንድ ነበሩ" እና "ቁስል እንኳን ሳይደርቅ እንዴት እንዲህ ይደረጋል?" የሚሉ አስተያየቶችን እየሰጡ እንደሆነ ታዘብኩ።

መንግስት ከጥቂት ሳምንታት እና ወራት በፊት በግድያ፣ በዝርፊያ፣ በእገታ እና በሽብር ሲከሰው ከነበረው አካል ጋር ስምምነት ሲፈፅም ረጋ ተብሎ እና በሰከነ ሁኔታ ካልተያዘ ጉዳት የደረሰባቸው እና በተለይ አሁን ድረስ ከታጣቂዎቹ ጋር በዱር በገደሉ ተፋጠው ላሉ የመንግስት ፀጥታ አካላት የሚያስተላልፈው መልዕክት ያሰጋል።

አለም አቀፍ ልምዶች እንደሚያሳዩት ከሁሉም በፊት የሚቀድመው የተሀድሶ ፕሮግራም ነው።

ሰላም ለሀገራችን።

Via ኤልያስ መሰረት

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

06 Dec, 14:34


ሀሰተኛ ፈጣን ሎተሪ ደርሶኛል በሚል የማጭበርበር ወንጀል የፈፀሙ ሁለት ግለሰቦችን መያዛቸዉን ፖሊስ ገለፀ

የቤንች ሸኮ ዞን ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር አዳነ አለማየሁ እንደገለፁት በሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር አማን ቀበሌ ህዳር 24 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 4:00 ሰዓት ሁለት ግለሰቦች ሆነዉ ሀሰተኛ ፈጣን ሎተሪ በመያዝ የግል ተበዳይዋን አማን ገበያ ላይ አግኝቷት የቢንጎ ሎተር ወጥቶልን በሚል ከባንክ 48,000፣ የእጅ ሞባይሏን፣የአንገት ወርቋን፣የጣት ቀለበቷን እና ወርቋን የጆሮ ወርቋን መዉሰዳቸዉን አስረድተዋል።

ግለሰቧን ምን እንዳስነኳት አለመታወቁን ያመለከቱት ፖሊስ አዛዡ ግለሰቧ ከ30 ደቂቃ በኋላ እንደተጭበረበረች ስለተረዳች ለፖሊስ በሰጠችዉ መረጃ ፖሊስ ተከታትሎ ሁለቱን ተጠርጣሪዎች ከ47,000፣የግል ተባዳይዋ የአንገት፣ የጣት፣የጆሮ ወርቅ እና ቴች ሞባይሏ ጋር በቁጥጥር ስር ዉለዉ ምርመራ እየተጣራባቸዉ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በመጨረሻም ምክትል ኢንስፔክተር አዳነ በሚዛን አማን ከተማ በተደጋጋሚ ጊዜ የሎተሪ ማጭበርበር ወንጀሎች እየተበራከተ በመሆኑ ህብረተሰቡ በመሠል አጭበርባሪዎች እንዳይታለል ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን ዘግቧል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

06 Dec, 10:54


ኡጋንዳዊ የአርሰናል ደጋፊ ከዩናይትድ ጋር ከነበረው ጨዋታ በኋላ በጥይት ተገደለ፡፡

የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊጉ ክለብ አርሰናል ደጋፊ የሆነው ኡጋንዳዊው ቡድኑ ማንቸስተር ዩናይትድን ከረታ በኋላ ደስታውን ሲገልፅ በጥይት ተመትቶ መሞቱ ተሰምቷል።

የአርሰናል ደጋፊው በአንድ የጥበቃ ሠራተኛ ተመትቶ መሞቱ ነው የተሰማው።

የጥበቃ ሠራተኛው ደስታቸውን እየገለፁ ያሉ የአርሰናል ደጋፊዎች ላይ በፈከተው እሩምታ ምክንያት አንድ ሌላ የአርሰናል ደጋፊም ቆስሏል።

ይህ የሆነው ሉካያ በተባለች ማዕከላዊ ኡጋንዳ በምትገኝ ከተማ ሲሆን፤ ከመዲናዋ ካምፓላ 100 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች።

አርሰናል ዩናይትድን አስተናግዶ 2-0 ሲረታ ጨዋታው ሊገባደድ ጥቂት ደቂቃዎች ሲቀሩት ነው የተኩስ እሩምታ የተከፈተው።

አንድ የአካባቢው ጋዜጠኛ ለቢቢሲ እንደተናገረው፤ የሕንፃው ባለቤት በደጋፊዎቹ ጫጫታ በመረበሹ ምክንያት የፀጥታ ሠራተኛው ፀጥ እንዲያስብላቸው ጠይቆት እንደነበር ነው።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

06 Dec, 10:47


#CBE ‼️

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 12 ሺህ ሰራተኞቹን ሊያሰናብት እንደሆነ ተሰማ‼️
ከሰሞኑ በፓርላማ የፀደቀው የመንግስት ሰራተኞች አዋጅን ተከትሎ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኞች ከስራቸው ሊሰናበቱ እንደሆነ ተጠቁሞ ነበር።

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት ሥራ ስምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ በአዋጁ አላማና አስፈላጊነት ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተው በነበሩበት ወቅት ስለ ሰራተኛ ቅነሳው ያነሱት ነገር ባይኖርም በመንግስት አቅጣጫ ከተያዘባቸው ጉዳዮች አንዱ "ከሚያስፈልገው በላይ የመንግስት ሰራተኛ አለ" የሚለው ዋናው መሆኑን ምንጮቻችን ጠቅሰው ነበር።

አዋጁ እንደ ፍርድ ቤት፣ አቃቤ ህግ፣ ፖሊስ፣ መከላከያ፣ እና ደህንነትን የመሳሰሉ ተቋማት ውስጥ የብሄር ስብጥር ለማድረግም ያለመ መሆኑን የጠቁሙት ምንጮች አዋጁ "የብሔር ብሔረሰቦች ብዙሃነት እና አካታችነት ስርዓትን ይገነባል" በሚል በመንግስት እንደታሰበ አስረድተዋል።

መሠረት ሚድያ በደረሰው አዲስ መረጃ ደግሞ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 12 ሺህ ሰራተኞቹን ሊያሰናብት እንደሆነ ሰምተናል።

ከሰሞኑ የባንኩ ሀላፊዎች በተለያዩ መርካቶ አካባቢ ባሉ ቅርንጫፎች ካሉ ሰራተኞች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት 12 ሺህ ሰራተኛ በቅርቡ እንደሚቀነስ እና ከተቀናሾች ውስጥ አንዱ እንዳይሆኑ ጠንክራችሁ ስሩ እንደተባሉ ሰራተኞቹ ጠቁመዋል።

"በቅርቡ ብዛት ያላቸው ቅርንጫፎች ስለሚታጠፉ በዚሁ አትቀጥሉም ተብለናል፣ እኛንም መግቢያ መውጫ አጥተናል" ያሉት ሰራተኞቹ እጣ ፈንታቸውን እየተጠባበቁ መሆኑን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ከሰሞኑ በመርካቶ አካባቢ ካለው የገቢዎች እና የነጋዴው አለመግባባት እና ከቀረጥ መጨመር ጋር ተያይዞ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ ተቀማጭ ገንዘቦች እየወጡ ነው ተብሏል። በተለይ ነጋዴዎች ገንዘባቸውን በብዛት ማውጣታቸው በመንግስት አካላት ጭምር ትኩረት ተሰጥቶት ውይይት እየተደረገበት እንደሆነ ታውቋል። ከዚህ ጋር ተያይዞ ከአንድ ቅርንጫፍ ማውጣት የሚቻለው የገንዘብ መጠን ላይ እቀባ ሊደረግ እንደሚችል ተገምቷል።
#መሠረት ሚዲያ
=====================
👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

06 Dec, 03:24


አዲስ አበባ

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትግራይ ክልል የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮች ጋር መወያየታቸው ተሰምቷል


📌በውይይቱ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዛዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እንዲሁም የህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ተገኝተው ነበር።

📌የውይይቱ ዝርዝር ይፋ ባይደረግም በክልሉ የሚታዩ ችግሮችን እንዴት በጋራ መፍታት እንደሚገባ ውይይት መደረጉ ተገልጿል።

📌በውይይቱ በተለዩ አንኳር ጉዳዮች ላይ በተቀመጡ የጋራ አቅጣጫዎች መሠረት በጋራ ለመስራትና የክልሉ ህዝብ የፀጥታ፣ የመልካም አስተዳደር እና የልማት ፍላጎት ለማሟላት አስቻይ ሁኔታ ለመፍጠር መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል።

📌ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ወደቀያቸው የሚመለሱበትን ሁኔታና ታጣቂዎችን ወደ መደበኛ ህይወት የመመለስ ሂደት በትኩረት የሚሰራበት እና የሚሳለጥበት ሁኔታ ላይ መግባባት ላይ መደረሱ ተገልጿል።

በተጨማሪ በክልሉ ያሉ የተፈጥሮ ሃብቶች አጠቃቀም ህጋዊ  በሆነ አግባብ የህዝብንና የሀገርን ጥቅም የሚያስጠብቅ እንዲሆን፣ ለህዝብ የሚቀርቡ የመንግስት አገልግሎቶች የሚሻሻሉበትና የህዝብን ፍላጎት የሚመጥኑ እንዲሆኑ ቀጣይነት ያለው ጠንካራ ስራ እንዲሰራ መግባባት ላይ መደረሱን ቲክቫህ ዘግቧል።

📌በዚሁ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት ውይይት ላይ ጊዚያዊ አስተዳደሩ ክልላዊ ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ያለበትን ሃላፊነት ለመወጣት በሚያስችለው አግባብ ላይም አቅጣጫ ተቀምጧል።

በርከት ያሉ አዳዲስ መረጃዎችን እዚህ ያገኛሉ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

05 Dec, 14:12


በሰሜን ወሎ ዞን በተፈፀመ የድሮን ጥቃት የ83 ዓመት እናት ተገደሉ

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ላስታ ወረዳ “ብልባላ” በተባለች መንደር ባለፈው ማክሰኞ ሌሊት በተፈፀመ የድሮን ጥቃት አንዲት የ83 ዓመት እናታቸው እንደተገደሉባችው የሟች ልጅ ተናገሩ።

ህዳር 24 ቀን 2017 ዓም ሌሊት 5፡30 አካባቢ በተፈጸመው ጥቃት ሌሎች ሁለት በግቢው ተከራይተው በሚኖሩ የጤና ባለሙያዎች ላይም የአካል ጉዳት ደርሷል ተብሏል።

በግቢያቸው ከነበሩ ክፍሎች መካክል ሶስቱ እንዳልነበር ሆነው ሲፈርሱ በጥቃቱ ከተመቱ ክፍሎች በአንዱ የነበሩት እናታቸው ሰጋቸው ተበጣጠሶ ህይወታቸው አልፏል ሲሉ ልጃቸው ቀሲስ ይትባረክ አድማሱ ተናግረዋል።

ቀብራቸው በወግ ባህል መስረት ፍትኃት ሳይደረግ መቀበራቸውን ያስታወቁት ልጃቸው ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ተጨማሪ ጥቃት ይደርሳል ከሚል ሰጋት ህብረተሰቡ ተሰብስቦ ሥርዓቱን ማከናወን ባለመቻሉ መሆኑን መግለፃቸውን የጀርመንድ ድምጽ በዘገባው አስታውቋል።

በመኖሪያ ቤቱ አካባቢም ሆነ በግቢው ውስጥ ታጣቂዎች እንዳልነበሩ የገለፁት ቀሲስ ይትባረክ፤ ግቢው ከዚህ በፊት የመኝታ አገልግሎት ይሰጥ እንደነበር ጠቅሰው ከሰሜኑ ጦርነት ወዲህ ግን ገበያው የተቀዛቀዘ በመሆኑ ከቤተሰብ የተረፉ ክፍሎችን ለመንግሥት ሠራተኞች ሲያከራዩ እንደነበር ተናግረዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media 🎙

05 Dec, 04:41


ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ ምሽት ላይ የሩስያ ፖሊስ ሞስኮ ውስጥ የሚገኙ የተለያዩ ባሮችን እና የምሽት መዝናኛ ክለቦችን ሲያስስ ነው ያደረው

አሰሳው ከግብረሰዶማውያን ፕሮፓጋንዳ ቁጥጥር ጋር የተያያዘ ነው።

በሩስያ ማንኛውም አይነት የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ማስተዋወቅ ወይም ፕሮፖጋንዳ መስራት በህገወጥነት መፈረጁ ይታወሳል።

ፖሊስ በቅዳሜ ምሽት አሰሳው በየባሩና በየምሽት ክለቡ እየገባ ጥብቅ ፍተሻ አድርጓል።

በወቅቱም ስማርት ስልኮች፣ ላፕቶፖች፣ የቪድዮ ካሜራዎች ተወርሰዋል።

በየመሸታ ቤቶቹ የተገኙ ሰዎች ዶክመንታቸው በፖሊስ ሲፈተሽ አድሯል።

የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ፤ የታገደውን የግብረሰዶማውያን እንቅስቃሴ ፖሮፖጋንዳ ሲያሰራጭ እንደነበር በተጠረጠረ አንድ በስም ባልገልጸው የምሽት ክለብ ውስጥም አሰሳና ፍተሻ መደረጉን ገልጿል።

Tikvah

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

23 Nov, 09:45


#የጥንቃቄ መልክት

በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የተሰጠ ውክልና የለም - የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

ለሥራ ዜጎችን እንልካለን በማለት የማጭበርበር ድርጊት የሚፈጽሙ አካላትን የሕግ ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራ እንደሚገኝም ገልጿል።

ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፤ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየዳረጉ መሆኑን ሚኒስቴሩ አመልክቷል።

መሰል የማጭበርበር ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ ሚኒስቴሩ ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና እንደሌለ ገልጿል።

ዜጎች በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ካላስፈላጊ ወጪ፣እንግልትና ከሌሎች አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ አሳስቧል።

ዜጎች የሁለትዮሽ ስምምነት በተፈረመባቸው መዳረሻ ሀገራት የሥራ ዕድል ለማግኘት (lmis.gov.et) የተሰኘውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በመመዝገብ ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ መሆን እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ ጠቁሟል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

23 Nov, 09:38


#በኮሬ ዞን ደመወዛቸው ያለአግባብ መቆረጡን የተቃወሙ ከ60 በላይ መምህራን ታሰሩ‼️

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ሳርማሌ ወረዳ ከፍላጎታቸው ውጪ ያለአግባብ ደሞዛቸው መቆረጡን የተቃወሙ ከ60 በላይ የሚሆኑ መምህራን መታሰራቸው ተገለጸ።

የመምህራኑ ደመወዝ ከነሐሴ 2016 ዓ.ም ጀምሮ መቆረጥ መጀመሩን እና እንዲመለስላቸው ጥያቄ ቢያቀርቡም ምላሽ አለማግኘታቸውን ተከትሎ የሥራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን የታሳሪ መምህራን ቤተሰቦች ለቪኦኤ አስታውቀዋል።

ባለቤታቸው መታሰሩን እና እስሩ ከመምህራኑ ተቃውሞ ጋር የተያያዘ መሆኑን ለጣቢያው የገለጹ ወ/ሮ አስቴር አበበ "ባለቤቴ ታስሮ ነው የሚገኘው፤ ወረዳው ደመወዛችን ይመለስ ብለን ብንጠይቅም እምቢ ብሎናል" ሲሉ ተደምጠዋል።

ይህን ተከትሎ ባለቤታቸውን ጨምሮ የታሰሩ በርካታ መምህራን በፖሊሶች ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ያስታወቁት ወ/ሮ አስቴር አበበ በድብደባው ቆስለው እስከአሁን ድረስ ህክምና ለማግኘት የተከለከሉ መምህራን መኖራቸውን ጠቁመዋል።

በወረዳው መምህር የሆኑት አቶ ወረደ ዋኪሶ በበኩላቸው መምህራኑ ከደመወዛቸው ላይ እስከ 25 በመቶ ያለአግባብ መቆረጡን አስረድተዋል።

በዚህም ምክንያት መምህራኑ አቤቱታቸውን በመምህራን ማሕበር አማካኝነት ለወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት እና ለወረዳው አስተዳደር ቢያቀርቡም "የምታመጡት ነገር የለም፤ እኛ የላክናቸው ካድሬዎች አስማምተው በመጡት መሰረት ነው ደመወዛችሁን የቆረጥነው።" የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።

የሳርማሌ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ጎሹ ጌታቸው የመምህራኑን መታሰር አረጋግጠው "መምህራኑ የታሰሩት ሌሎች መምህራን እንዳያስተምሩ በማሳመጻቸው" ነው ብለዋል።
VOA
👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

23 Nov, 07:01


#AddisAbaba ‼️

ለ 614 ጫኝ እና አውራጆች ፍቃድ ተሰቷል።

በከተማዋ 614 የጫኝ እና አዉራጅ ማህበራት ህጋዊ ፍቃድ አግኝተዋል ተባለ።

በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ዘንድ የምሬት ምንጭ ሆኖ የቀጠለዉ የጫኝ እና አዉራጅ አደረጃጀት ህጋዊ አካሄድ እንዲኖረዉ እየተደረገ ነዉ ተብሏል።

ከአንድ አመት ወዲህ የጫኝ እና አዉራጅ ማህበራት መመሪያ ህግ እንዲወጣ መደረጉ ተነግሯል።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ ሚደቅሳ ከበደ የከተማዋ መታወቂያ አላቸዉ የተባሉ 7228 ወጣቶችን ወደ ስራ ማስገባት መቻሉን ሰምተናል።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላም እና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እየመራዉ ነዉ በተባለዉ መመሪያ በእያንዳንዱ እቃዎች የመጫን እና የማዉረድ ሂደት  ላይ የገበያ ጥናት የተደረገበት የዋጋ ተመን ማዉጣቱን የቢሮዉ ምክትል ሀላፊው አቶ ሚደቅሳ ተናግረዋል።

ሆኖም በአዲስ አበባ ከተማ የልማት ተነሺዎችን ተከትሎ የሚጠየቁ የጫኝ እና አዉራጅ የዋጋ ተመን ክፍያዎች በህብረተሰቡ ዘንድ ቅሬታ ተነስቶበታል።

ቢሮዉ በዚህ ዙሪያ ያሉ የቁጥጥር ክፍተቶችን ለማስተካከል ምን እየሰራ ነዉ ብለን ላነሳንላቸዉ ጥያቄ " ህጋዊ ማህበራቱ ለባለንብረቶች ንብረት ሀላፊነት እንዲወስዱ በማስገደድ  እንዲሁም የዋጋ ጭማሪ እንዳያደርጉ ክትትል እያደረኩ ነዉ" ሲል ምላሽ ሰጥቷል።

በከተማዋ አራብሳ እና ከከተማዋ መውጫ ላይ የሚገኙ ሰፈሮች ህገወጥ  የጫኝ እና አዉራጅ አደረጃጀቶች በስፋት መታየታቸዉ ሰምተናል።

ይህንን ተከትሎ ማህበረሰብ ለአገልግሎቱ ህጋዊ ደረሰኝ እንዲጠይቅ ያስፈልጋል ተብሏል።

ሆኖም ህብረተሰቡ ንብረቱን ከጫኝ እና አዉራጅ አካላት ዉጪ በራሱ አቅም የማዉረድም ሆነ የመጫኝ ሙሉ ፍቃዱ ተሰቶታል።

ማህበረሰብ ይህን ያልተከተሉ ማህበራት በተመለከተ የአዲስ አበባ ፖሊሲ ኮምሽን ነፃ የስልክ መስመሮችን በመጠቀም ጥቆማዎችን መስጠት የሚችሉ መሆኑን ቢሮዉ አሳዉቋል።

(ethio fm)

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

23 Nov, 05:41


ሩሲያ ወደ ዩክሬን የተኮሰችው “ኦሬሽኒክ” የተሰኘው ሚሳኤል በርካታ የአውሮፓ ሀገራትን በ20 ደቂቃ ውስጥ መምታት የሚችል ነው ተባለ፡፡

“ኦሬሽኒክ” ሚሳኤል በዲንፒሮ የሚገኘውን የሚሳኤል ማምረቻና የጦር መሳሪያ መጋዝን ማቃጠሉን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል፡፡

ዩክሬን ረጅም ርቀት ሚሳኤሎችን ተጠቅማ ሩሲያን እንድታጠቃ የፈቀዱት አሜሪካ እና ብሪታንያ፥ አዲሱ ሚሳኤል የኒዩክሌር አረር መሸከም የሚችልና አውሮፓን ኢላማ ለማድረግ የተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል።

ከሩሲያ ጀርመን ለመድረስ 14 ደቂቃ ብቻ እንደሚበቃው የተነገረለት “ኦሬሽኒክ” በ40 ደቂቃዎች ውስጥ በአሜሪካ ያሉ ኢላማዎችን መምታት እንደሚችል ተገልጿል።

ስለሩሲያው አዲስ ሚሳኤል “ኦሬሽኒክ” በቀጣዩ ሊንክ ተጨማሪ ያንብቡ፦ https://bit.ly/3CEGyF7

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

23 Nov, 04:28


አንድ ጊዜ የሚያገለግሉ የፕላስቲክ ምርቶች ወደ ሀገር ቤት እንዳይገቡ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅ ለምክር ቤቱ ተመራ ‼️

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ለአንድ ጊዜ ግልጋሎት የሚውሉ የፕላስቲክ ምርቶች ወደ ሀገር ቤት እንዳይገቡ የሚከለክል ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መምራቱ ተገለጸ።ረቂቅ አዋጁ በሀገሪቱ የደረቅ ቆሻሻ አሰባሰብ፣ አጓጓዝ፣ አከመቻቸት፣ መልሶ አጠቃቀም፣ መልሶ ኡደት እና አወጋገድ ላይ ሥርዓት እንዲኖር ያደርጋል ሲሉ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ዳይሬክተር ኢንጂነር ሌሊሴ ነሜ ተናግረዋል።

ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተመራው ረቂቅ አዋጁ የዜጎችን በንጹሕ እና ጤናማ አካባቢ የመኖር መብት ለማረጋገጥ የላቀ ፋይዳ እንዳለውም ተገልጿል።በተጨማሪም የሀገሪቱን ዕድገት፣ የከተሞችን መስፋፋት እና እየጨመረ የመጣውን የህዝብ ቁጥር የሚመጥን ዘመናዊ የቆሻሻ አወጋገድ ሥርዓት ለመፍጠር እንደሚያግዝም ዋና ዳይሬክተሯ ለኢቢሲ አመላክተዋል።

አዋጁ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቆ ወደ ሥራ ሲገባ በዜጎች ጤና እና በስነ-ምህዳር ላይ ከባድ አሉታዊ ተጽእኖ እያሳደረ የሚገኘውን የፕላስቲክ ምርት ጉዳት ለመቀነስ እንደሚያግዝም አስገንዝበዋል።
Via yenetube

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 17:31


#ኦሮሚያ ክልል ለወታደራዊ ስልጠና የሚደረግ አስገዳጅ ምልመላ መባባሱን ነዋሪዎች ገለጹ ‼️
በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች ለወታደራዊ ስልጠና በግዳጅ የሚወሰዱ ወጣቶች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመሩን ነዋሪዎች ተናገሩ።

ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ በሰሜን ሸዋ ዞን ያያ ጉለሌ ወረዳ የፍታል ከተማ ነዋሪ ተማሪዎችን እና አርሶ አደሮችን ጨምሮ ከ250 በላይ ሰዎች በግዳጅ ወደ ወታደራዊ ስልጠና መወሰዳቸውን ገልጸዋል።

በ #አዳማ ከተማ ነዋሪ የሆኑ አንዲት እናት ህዳር 2 ቀን 2017 ዓ.ም የ17 አመት ልጃቸው ጌታቸው ተድላ ሂሪጎ በመንገድ ላይ ቆሎ እየሸጠ በነበረበት ወቅት በፖሊስ መታሰሩን ለማስለቀቅ 30,000 ብር መክፈል ባለመቻላቸው ልጃቸው ለውትድርና ስልጠና መወሰዱን አስረድተዋል።

በተመሣሣይ በጅማ ዞን ሰጠማ ወረዳ የግጦሽ ቦታ ለባለሀብቶች መሰጠቱን የተቃወሙ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ቤተሰቦቻቸው እስከ 70,000 ብር እንዲከፍሉ የተጠየቀባቸው ሲሆን መክፈል የማይችሉ ከሆነ ግን “ወታደራዊ ግዳጅ እንደሚጠብቃቸው” ነዋሪዎች ገልጸዋል።
#አዲስስታንዳርድ #Oromia
👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 17:21


#መረጃ ❗️❗️

በአማራ ክልል በተለያዩ መጠለያዎች የተጠለሉ ኤርትራዊያንና ሱዳናዊያን


ስደተኞች ደኅንነታቸው አደጋ ላይ መውደቁን መናገራቸውን ኒው ሂውማኒተሪያን ድረገጽ ዘግቧል። ስደተኞቹ ታጣቂዎች ጥቃት እንደሚፈጽሙባቸውና የግዳጅ ጉልበት እንደሚያሠሯቸው መግለጣቸውን ዘገባው አመልክቷል። በደቡብ ጎንደር ዞን ደምቢያ ወረዳ በሚገኘው አለምዋች መጠያ የተጠለሉ ኤርትራዊያን ስደተኞች፣ የታጠቁ ኃይሎች አካላዊ ጥቃትና ዘረፋ እንደሚፈጽሙባቸው፣ አፍነው እንደሚወስዷቸውና ባንድ ዓመት ውስጥ ዘጠኝ ስደተኞች በጥይት ተመትተው እንደሞቱ ዘገባው ጠቅሷል። በተመሳሳይ ጊዜ ውስጥ ሰባት ሕጻናትን ጨምሮ 12 ስደተኞች ታግተው፣ ለማስለቀቂያ ግማሽ ሚሊዮን ብር እንደተጠየቀባቸው የመጠለያው አመራሮች ተናግረዋል ተብሏል።
via wazema

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 17:20


አትሌት ሰውመሆን አንተነህ ''ስፔሻል ዐይን''ተገጠመለት ‼️

አትሌት ሰውመሆን አንተነህ ሙሉ ወጪው ተሸፍኖለት ወደሕንድ ሀገር ተጉዞ ''ስፔሻል ዐይን'' ሊገጠምለት እንደሆነ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን መግለፁ ይታወቃል።

የ17 ዓመቱ አትሌት ሰውመሆን ታሪኩ ፔሩ ሊማ በተካሄደው የዓለም ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በአምስት ሺሕ ሜትር ሀገሩን ወክሎ እንዲወዳደር አንደኛ ሆኖ ተመርጦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ባዘጋጀው ሆቴል ገብቶ በዝግጅት ላይ እያለ ልምምዱን ለመሥራት ወደ ጫካ በወጣበት አንድ ዕለት ፖሊስ ነኝ ካለ አንድ ሰውና ከሁለት ግብራበሮቹ ጋር በተፈጠረ እሰጣ ገባ አንድ ዐይኑን በሽጉጥ ተመትቶ ብርሃኑን እንዳጣ የሚዘነጋ ይታወሳል።

አትሌቱ ከገጠመው ከፍተኛ ጉዳት ለማገገም በዳግማዊ ምኒልክ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሕክምናውን ሲከታተል ቆይቶ፣ በኋላም ሙሉ ወጪም በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ተሸፍኖ ለተሻለ ሕክምና ወደሕንድ ሀገር እንደሚጓዝ መነገሩም ይታወሳል።

በወቅቱ በሕንድም በመጀመሪያ ዙር ለሰባት ቀን ሕክምና ተደርጎለት እንደሚመለስና ከሁለት ወር በኋላ ''ስፔሻል ዐይን'' ለማስገጠም ተመልሶ እንደሚሄድ ተገልፆ ነበር።

ከሰሞኑም ለዚህ ሕክምና አትሌቱ ወደሕንድ እንዳቀና የሚታወቅ ሲሆን በእዚህም መሰረት ለአትሌት ሰውመሆን ''ስፔሻል ዐይን'' እንዳስገጠመለት የሚጠቁም መረጃ በአትሌቱ የማኅበራዊ ትሥሥር ገፅ ላይ ተጋርቷል።
አትሌቱም ከአጋራው ፖስት ስር''ተመስገን አምላኬ ሁሉም ታሪክ ሆነ።'' የሚል መልዕክት አስፍሯል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 12:04


BreakingNews‼️

መንግሥት ሁለት ታዋቂ የሰብአዊ መብት ድርጅቶችን አገደ

የሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን በሰብአዊ መብት ሥራዎች ታዋቂ የሆኑ ድርጅቶችን በደብዳቤ ማሸጉን ዋዜማ አረጋግጣለች። ከታገዱት ድርጅቶች መካከልም “የመብቶች እና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል” (በእንግሊዝኛ ምህጻረ ቃሉ “CARD” እና “ስብስብ ለሰብአዊ መብቶች ኢትዮጵያ” (AHRE) ይገኙበታል።
ባለሥልጣኑ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እና በዚህ ሳምንት ለድርጅቶቹ በተናጠል በላከው ደብዳቤ፣ ድርጅቶቹ ከማንኛውም እንቅስቃሴ መታገዳቸውን አስታውቋቸዋል። 

ዋዜማ የተመለከተችው ደብዳቤ ለእገዳው የሰጠው ምክንያት “ከፖለቲካ ገለልተኛ ሆኖ መሥራት ሲገባው ከዓላማው ውጭ በመንቀሳቀስ የአገርና የህዝብ ጥቅምን የሚጎዱ ተግባራት ላይ በመሰማራቱ ከባድ የህግ ጥሰት መፈጸሙን ማረጋገጥ ተችሏል” የሚል ነው። ዋዜማ የደረሳት መረጃ የታገዱት ድርጅቶች ቁጥር ከሁለት እንደሚበልጥ ቢጠቁምም፣ ለጊዜው ማረጋገጥ አልቻልንም።

ይህ እርምጃ መንግሥት በሰብአዊ መብት ጉዳዮች ላይ በሚሠሩ ድርጅቶች ላይ ሲያደረግ የቆየው ጫና የመጨረሻ ከፍታ ነው ሲሉ ስለጉዳዩ በቅርብ የሚያውቁ ምንጮች ለዋዜማ ተናግረዋል። የእግድ እርምጃው በድርጅቶቹ መሪዎች አካባቢ የተጠበቀ እንዳልነበር ለመረዳት ችለናል።

የሲቪል ማህበረስበ ድርጅቶች ባለስልጣን መያዶችን የማገድ ስልጣን ቢኖረውም “የአሁኑ እርምጃ በሕጉ የተዘረዘረውን ቅደም ተከተልና ቅድመ ሁኔታ የሚጥስ ነው” ብለዋል ሌላ የሕግ ባለሞያ። ድርጅቶቹ እግዱን በሕግ የመቃወም መብት ይኖራቸዋል።

ለባለሥልጣኑ ቅርብ የሆኑ የዋዜማ ምንጮች እገዳው የተላለፈበት ሂደት ለእርሱም ግልጽ እንዳልሆነ ተናግረዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ ድርጅቶቹን እና ባለሥልጣኑን ለማነጋገር እየሞከርን ነው።

[ዋዜማ]

==============================
ተጨማሪ መረጃዎች እንዲደርሳችሁ ከስር የሉ Link join አድርጉ፣ለሌሎች ጋብዙ👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 11:33


#መረጃ‼️

ፖለቲከኛው  ጀዋር መሃመድ ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አሰቃቂ  ግድያን አስመልክቶ አቋማቸውን አሳውቀዋል

ሰሞኑን ተገደለ ሰለተባለው ወጣት አስተያየት የሰጡት ጀዋር መሃመድ ለዚህ ሁሉ ምንጩ በሃገሪቱ እየተደረጉ ያሉ ጦርነቶች ናቸው ብለዋል ፡፡

ለእነዚህ ሁሉ ጦርነቶች እና ግጭቶች ዋነኛው ተጠያቂ በስልጣን ላይ ያለው  መንግስት ነው ሲሉ ጀዋር መሃመድ  የተናገሩት ፡፡
(አንኳር መረጃ)

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 04:51


በኦሮሚያ ክልል በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መካከል የሚደረግ ግጭት እና ጦርነት መቀጠሉ የህዝቡን መከራ እና ሰቆቃ አባብሶታል።

የጦርነቱ ገፈት ቀማሽ የሆነው ህዝብ ፤ ግድያ እና መፈናቀልን ጨምሮ ጦርነቱ ያደረሰበት ቀውስ እንዲያበቃ በአደባባይ ድምጹን አሰምቷል።

በመንግስት እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መካከል ከአንድም ሁለት ጊዜ ከሀገር ውጭ የተሞከረው የሰላም ንግግር አልሰመረም ። ህዝቡ ተፋላሚዎች ለሶስተኛ ጊዜ ተገናኝተው ችግሩን በሰላም ይፈታሉ ብሎ በሚጠብቅበት በአሁኑ ወቅት ሁለቱም ወገኖች በየራሳቸው መንገድ የአስገዳጅ የአዳዲስ ወታደር ምልመላ እና አፈሳ እያከናወኑ ነው የሚል ስሞታ ይሰማል።

ይህ ደግሞ የሰላም ጥሪ የሚያሳተጋባውን የክልሉን ነዋሪ ተስፋ ከማሳጣት አልፎ ክልሉን ብሎም ሀገሪቱን ለተጨማሪ የቀውስ ዓመታት እንዳይጋብዝ አስግቷል።

  https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 04:22


🍫 እንደ ተመራማሪዎች ከሆነ ጥቁር ቸኮሌት የደም ዝውውር በጣም አስፈላጊ ወደሚባሉ የአንጎል ክፍሎች እንዲፈስ ያበረታታል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

22 Nov, 04:17


#Bitcoin

የአንድ ቢትኮይን ዋጋ ከ98,000 ዶላር በላይ ሆነ።

" የመጀመሪያው የክሪፕቶ ፕሬዝዳንት " የተባሉትና " አሜሪካን የፕላኔታችን የክሪፕቶከረንሲ መዲና አደርጋታለሁ " ያሉት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት መሆናቸው ከተረጋገጠ በኃላ ቢትኮይን ወደላይ ተተኩሷል።

ዛሬ የተመዘገበው የቢትኮይን ዋጋ በታሪክ ከፍተኛ ሆኗል።

አንድ የቢትኮይን ዋጋ 98,149 የአሜሪካ ዶላር ገብቷል።

ትራምፕ በምርጫ ቅስቀሳቸው ወቅት " በፍጹም ቢትኮይናችሁን አንዳትሸጡ  " ሲሉ ለክሪፕቶ ማህበረሰቡ መልዕክት አስትላልፈው ነበር።
Via:tikvah

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

18 Nov, 06:12


ከኤርትራ ጋር እርቅ ማውረድ እንፈልጋለን - ጌታቸው ረዳ ‼️

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ፤ ትግራይ ከኤርትራ ጋር እርቅ ማውረድ እንደምትፈልግ ላንድ የጣሊያን የዜና አውታር ተናግረዋል።

በአንድ የጤና ጉባዔ ላይ ለመገኘት ጣሊያን የሚገኙት አቶ ጌታቸው፤ በጦርነቱ ለተፈጸሙ ወንጀሎች ተጠያቂነት ለማስፈን የፍትሕ ዓለማቀፋዊ ሥርዓት ማቋቋም እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

ለወንጀሎች ሃላፊነትና ተጠያቂነት ሳይኖር፣ ከኤርትራ ጋር መደራደር እንደማይቻል ግን አቶ ጌታቸው አስምረውበታል።

አቶ ጌታቸው ረዳ በትግራይና አማራ ክልሎች መካከል ምዕራብ ትግራይ ላይ ያለው ውዝግብ በሰላም ይፈታ እንደኾነ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ ዘላቂ ሰላምን ማስፈን ከተፈለገ ሌላ አማራጭ የለም በማለት ጌታቸው መልሰዋል።

avvenire.it/mondo

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

18 Nov, 03:28


አይ ኢቢሲ Fact Check፣ አይ ማስተባበል!

ክስተቱን በአይን ያዩ የኤርፖርት ሰራተኞች፣ የሲቪል አሺዬሽን ባለሙያዎች፣ የአየር መንገድ ባልደረቦች እና አንዳንድ ተጓዦች ጭምር እውነት እንደነበር ትናንት አረጋግጠውልኝ ነበር።

ለማስተባበል የተሄደበት "ልምምድ ነበር" የሚለው ምላሽ ይባስ ብዙ ጫና ላይ ያለውን አንድ ለእናቱ የሆነውን አየር መንገዳችንን ሌላ ችግር ላይ መጣድ ነው።

ደሞ ልምምድ የሚደረገው በፕሮግራም በአየር ጦር ቤዝ እንጂ ኤርፖርት ገብተው ሊሳፈሩ check in ያረጉ ሰዎችን ወደ ቤታቸው መልሰህ ነው እንዴ?

ይህን ውሸት ሰምተን ሌላ ምን ቢነግሩን እንመን?

@EliasMeseret

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 16:00


የሂዝቦላህን የሚዲያ ሃላፊ ተገደለ

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስቴር የሂዝቦላህ የሚዲያ ሃላፊ የሆነውን ሞሃመድ አፊፍ ሰይድን መግደሉን አስታውቋል፡፡

የእስራኤኤል ጦር በዛሬው ዕለት በማዕከላዊ ቤሩት የሂዝቦላህ ደጋፊ የሆነ የፖለቲካ ፓርቲ ሕንጻ ላይ የአየር ጥቃት መፈጸሙን ሬውተርስ ዘግቧል፡፡

በጥቃቱም ለልዩ ስብሰባ ሕንጻው ውስጥ የነበረው የሂዝቦላህ የሚዲያ ሃላፊ ሞሃመድ አፊፍ መገደሉ ነው የተገለጸው፡፡

ሞሃመድ አፊፍ በቅርቡ በእስራኤል ጥቃት የተገደለው የቡድኑ የቀድሞ መሪ ሃሰን ነስራላህ የሚዲያ ጉዳዮች አማካሪ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

በሊባኖስ በሚዲያ ግንኙነት ጉዳዮች ዙሪያ አንቱታን ያተረፈ የቡድኑ ቁልፍ ሰው እንደነበርም ዘገባው አመላክቷል፡፡

በሌላ በኩል የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት በሰሜን ጋዛ በፈጸመው ጥቃት የ72 ዜጎች ሕይወት ማለፉን ተሰምቷል፡፡

ቤይት ላሒያ በተሰኘ ግዛት በሚገኝ ባለብዙ ፎቅ መኖሪያ ሕንጻ ላይ በተፈጸመው ጥቃት ከሞቱት በተጨማሪ በርካታ ዜጎች መጎዳታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታውቀዋል፡፡

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 15:15


https://www.tiktok.com/@noralemtube1/video/7438262325657849144?_r=1&u_code=e0lg2ef75i2ai9&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=ec157e829dkk3d&share_item_id=7438262325657849144&source=h5_m&timestamp=1731856515&user_id=7077185647011152901&sec_user_id=MS4wLjABAAAAeBA_BYMAEd2PX_qli8unwm8BSO2_zQiQ1_eEZzMIzwxqqZP-t_15hZgr0w1rU13O&social_share_type=0&utm_source=telegram&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7434599300442785591&share_link_id=6f8fe4a2-f591-4981-81f4-8960486b6769&share_app_id=1233&ugbiz_name=MAIN&ug_btm=b8727%2Cb2878&link_reflow_popup_iteration_sharer=%7B%22click_empty_to_play%22%3A1%2C%22dynamic_cover%22%3A1%2C%22follow_to_play_duration%22%3A-1.0%2C%22profile_clickable%22%3A1%7D&enable_checksum=1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 13:34


🇹🇩🇷🇺 ሶስት የሩሲያ እና አንድ የቤላሩስ ዜጋ በቻድ ከሚገኝ እስርቤት ከሳምንታት ቆይታ በኋላ ተለቀቁ

ከታሳሪዎቹ አንዱ የነበረው የሶሾሎጂስቱ ማክሲም ሹጋሌ የስራ ባልደረባ "ሶስት የሩሲያ እና አንድ የቤላሩስ ዜጋ በቻድ ለሁለት ወር ያህል በእስርቤት ከቆዩ በኋላ ተለቅቀው ዛሬ ማታ ሞስኮ ገብተዋል"  በማለት ለስፑትኒክ ተናግሯል።

ባለፈዉ መስከረም 19 የተያዙትን የሩሲያ እና የቤላሩስ ዜጎች አስመልክቶ በወቅቱ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከእስር መፈታታቸው እስኪረጋገጥ ድረስ አስፈላጊውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልፆ ነበር። የሹጋሌ የስራ ባልደረባ ለስፑትኒክ ጨምሮም በተያዙበት እለት እንዳናገራቸው ነገርግን በኢንጃሜና አየር ማረፊያ ከደረሰ በኋላ ድንበሩን ማለፍ እንዳልቻለ አስረድቷል። 

ባለፈዉ መስከረም 25 በሩሲያ የቻድ አምባሳደር የሆኑት አደም ባቺር ፦  የቻዱ ፕሬዚዳንት መሀመት ኢድሪስ ዴቢ እስረኞቹ እንዲፈቱ መወሰናቸውን ለስፑቲኒክ ተናግሮ ነበር።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 11:32


#update ‼️

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 11:31


የሜክሲኮው አሰልጣኝ ሀቪየር አጉሬ..... ‼️
ቡድናቸው በ ሆንዱራስ መሸነፏን ተከትሎ ከደጋፊዎች በተወረወረ ኩባያ እንዲህ ተፈንክተዋል 🤕

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 11:29


በቀብር ስፍራ በመገኘት የቲክቶክ ቪዲዮ ሲሰሩ የቆዩ ወጣቶች በፖሊስ ተያዙ ‼️

I በቀጨኔ ወረዳ 4 ቀጨኔ ዘላቂ ማረፊያ በሚባለው የቀብር ቦታ በመገኘት ሙዚቃ በመክፈት የቲክቶክ ቪዲዮ እየሰሩ ሲለቁ የነበሩ ወጣቶች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፖሊስ አስታወቀ።

በቁጥጥር ስር ከዋሉት ወጣቶች መካከል አንዱ ድርጊቱን የፈፀምነው ተመልካችን ለማዝናናት ብለን ነበር ተጠያቂ እንደሚያደርግ ባለማወቃችን ስህተት ፈፅመናል ብሏል።

ድርጊታቸው በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ አንቀጽ 493 የሙታንን ሰላም እና ክብር መንካት በሚል እንደሚያስጠይቅ ከዚህ ቀደም መምህር፣ ጠበቃና የህግ አማካሪ አበባየሁ ጌታ መረጃን አካፍለን ነበር።
via_Fast Merja

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 11:21


#Update

በቁጥጥር ስር ውሏል

በመርካቶ ጃቡላኒ ህንፃ ድንች ላይ የእሳት ቃጠሎ ከቀኑ 6:30 ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር መዋሉን ሰምተናል::

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 09:39


#BreakingNews ‼️
#Russian
#Ukraine ‼️

የሩሲያ ከፍተኛ የአየር ድብደባ በሁሉም የዩክሬን ግዛቶች!

የዩክሬን-ሩሲያ ጦርነት በይፋ ከተጀመረ ወዲህ ሩሲያ ከፍተኛ ነው የተባለውን የአየር ድብደባ የዩክሬን የሀይል ማመንጫዎችን ኢላማ በማድርግ ጥቃት መፈጸሟ ተነገረ፡፡

ሩሲያ120 ሚሳኤሎችን እንዲሁም 90 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በመጠቀም በሁሉም የዩክሬን ግዛቶች ጥቃት መፈጸሟን የዩክሬኑ ፕሬዝዳት ቭሎድሚር ዜሌንስኪ አስታውቀዋል፡፡

ፕሬዝዳንቱ ሞስኮ የሀገሪቱን የሀይል ማመንጫ መሰረተ ልማቶችን ኢላማ በማድርግ ጥቃቱን መፈጸሟን ነው በቴሌግራም ገጻቸው ያሰፈሩት፡፡

በዚህም ጥቂት በማይባሉ የዩክሬን አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ሀይል መቋረጡን ይፋ አድርገዋል፡፡

ዜሌንስኪ የሀገራቸው አየር መከላከያ 140 የሚጠጉ ኢላማዎችን ማምከኑንም ተናግረዋል፡፡

በጥቃቱ በማይኮላይቭ ግዛት ሁለት ሴቶች የተገደሉ ሲሆን፤ በመካከለኛው ዩክሬን ደግሞ ሁለት የባቡር መንግድ ሰራተኞች መገደላቸውን ሀገሪቱ አስታውቃለች ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 08:52


ችግሩ ተፈትዋል…???


ለ ዓመታት የቆየ መፍትሔ ማይገኝለት የመሰለ ችግር ባልተጠበቀ ጊዜ እና ባልታሰበ ሁኔታ መፍትሔ አግኝቷል ከ ሰሞኑን በ ዲ/ን አቤኔዘር ውብሸት በtiktok ቤተሰቦቹ አማካኝነት በጊንጪ ደንዲ ወረዳ የሚገኘው 116 ዐመት ያስቆጠረው የጋሬ ደብረ ሰላም አቡነ ተ/ሀይማኖት ቤ/ክ በአዲስ መልኩ ታድሶ ከተመረቀ የቅርብ ቀን ትውስታ ነው።


ለአመታት ከ 10 የማይበልጡ አባ ወራዎች በአካባቢያቸው ላይ ያለው ባዶ ቦታ ላይ መስቀል በመትከል በየወሩ በ24 በቦታው ላይ ተሰባስበው ተክልዬን ይዘክሩ ነበር ሰው ከሞተም ፍትሐት ሳይፈታ ባዶ ቦታውን እንደ ቤተ ክርስትያን በመጠቀም ይቀብሩ ነበር ይሄም ቤ/ክ ስለሌላቸው ቁጡራቸው በጣም ጥቂት በመሆን ይቸገሩ የነበሩ አባቶች እና እናቶች በብዕፁ አባታችን አቡነ ይስሐቅ በወላይታ ሶዶ ሀገረ ስብከት ሊቀ ዻዻስ መልካም ፍቃድ እና ክትትል እንዲሁም በዲ/ን አቤኔዘር ውብሸት የtiktok ቤተሰቦች ሙሉ የግንባታ ወጪ በመሸፈን ለአመታት የተክልዬ ቤተ ክርስትያን ነው ብለው በባዶ መሬት ላይ ያለ ቤተ መቅደስ ፀሎት ሲያደርጉ የነበሩ 10 የሚሆኑ አባ ወራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የተክልዬ ቤ/ክ ተሰርቶ በዛሬው እለት በቀን 08/03/2017 ተመርቋል።


የዚህ ቦታ መገኛውም በወላይታ ሶዶ ሀገረ ስብከት በሁምቦ ወረዳ የኮይሻ ጎላ ኦቤያ አቡነ ተ/ሀይማኖት ቤ/ክ ነው  ልብ በሉ ቤተ ክርስቲያን የወርቅ ወይም የነሐስ ማቅለጫ ቦታ አይደለችም፤ ለቅድስና የተጠሩ ሁሉ እና የመላእክት ኅብረት እንጂ፡፡ስለዚህ ከስጦታችሁ በፊት ልባችሁን ይዛችሁ ኑ፡፡

ለዝያም ነው ለዘመናት ንፁህ ልብ ይዘው የፈጣሪ ቤት አንድ
ቀን እኛ ጋር ይመጣል ብለው በእምነት ሲፀልዩ የነበሩ 10 ብቻ የሚሆኑ አባ ወራዎች ዛሬ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነው  የቤ/ክ ባለቤት የሆኑት::

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

17 Nov, 07:40


#GreatEthiopianRun 🇪🇹

የ 2017 የሶፊ ማልት ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የአለም አቀፍ የ 10 ኪሎ ሜትር ውድድር ለሀያ አራተኛ ጊዜ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

የወንዶች የ 10 ኪሎ ሜትር ውድድሩን ቢኒያም መሀሪ 28:25.661 በሆነ ሰዓት በመግባት በአንደኝነት አጠናቋል።

አትሌት ቢኒያም መሀሪ ለተከታታይ ሁለት አመታት የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የወንዶች 10 ኪሎ ሜትር ውድድር አሸናፊ መሆን ችሏል።

የሴቶቹን 10 ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት አሳየች አይቸው 32:13.418 በሆነ ሰዓት በአንደኝነት ማጠናቀቅ ችላለች።

የውድድሩ አሸናፊዎች ስንት ያገኛሉ ?

በሁለቱም ጾታዎች በውድድሩ

- 1ኛ. ለወጡ አትሌቶች 250,000 ብር

- 2ኛ. ለወጡ አትሌቶች 150,000 ብር እንዲሁም

- 3ኛ. ሆነው ለጨረሱ አትሌቶች 100,000 ብር የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 16:14


https://vm.tiktok.com/ZMhGsLJLL/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 15:48


አንድ ጅብ በአራት ሰዎች ላይ ጉዳት አደረሰ‼️
ትላንት ከአዲስ አበባ 24KM ርቀት ላይ ሰበታ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ አንድ ጅብ ከወንዝ አቅጣጫ ገባ ወጣ አያለ ልጆችን እያስደነገጠ እሱም አልበቃ ብሎት የሰዉ ማድቤት በመገባት ሲያስቸግር በጊዜዉ እርምጃ ሳይወሰድበት ማታ ላይ እንደገና ሮጦ ከገባበት ወንዝ ዉስጥ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ተኩል አካባቢ ላይ በመዉጣት የሰዉ በር ላይ ያገኘዉን የሰፈሩን መንገደኛ እድሜዉ 35 አመት የሚገመት ሰዉ የእጁን መዳፍ እንዲሁም አምስት ቦታ በመንከስ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰበት ሲሆን ተጎጂዉ የአስጥሉኝ ጩኀት ሲጮህ እሱን ሊያስጥሉ በራቸዉን ከፍተዉ በወጡ ቤተሰቦች ቤት በመግባት 3 ( ሶስት) እድሚያቸዉ ከ25-30 የሚገመቱ እህታማቾችን በመንከስ ጉዳት አድርሷዋል፡፡

በመጨረሻም በህበረተሰቡ ርብርብ ጅቡ የተገደለ ሲሆን የእንሰሳት ሀኪሞች ባደረጉት ምርመራ ጅቡ ታማሚ እንደሆነ ያረጋገጡ ሲሆን በሽታው ወደ ሰዎቹ እንዳይተላለፍ በጅቡ ጉዳት የደረሰባቸዉንና ለመግደል የተሳተፉትን ብሎም በአካባቢዉ የሉትን ህብረተሰቦች የክልሉ ጢና ቢሮ ክትባት እንደሚሰጣቸዉ የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል፡፡ በተለይ በከተማ ዳርቻ ላይ የሚኖሩ ሰዎች ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ጠቁመዋል።
Via:አዩ
👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 15:43


🇪🇹✈️ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ2024 የቢዝነስ ተጓዦች ሽልማት የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ ተብሎ ተመረጠ

"የ2024ቱን የቢዝነስ ተጓዦች ሽልማት ለተከታታይ አምስት ዓመታት በማግኘታችን ደስተኞች ነን። ይህ ሽልማት የቡድን አባላቶቻችንን እና ተልዕኳችንን ያለችግር እንድንፈጽም ከእኛ ጋር ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሰሩ ባለድርሻ አካላትን ቁርጠኝነት፣ ትጋት እና ልፋት የሚያረጋግጥ ነው" ሲሉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው በሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት ተናግረዋል።

ቢዝነስ ትራቭለር፤ ለስራ ወደ ውጭ ሀገር የሚበሩ ተጓዦችን ትኩረቱ ያደረገ በዓለም የታወቀ መጽሔት ነው። በመጽሔቱ ይፋ የሚደረገው አሸናፊ አብዛኛውን ግዜ በአንባቢዎች ድምጽ እና በገለልተኛ የኦዲት ኩባንያ ይወሰናል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 15:42


🇷🇺🇪🇬 የሩሲያ እና ግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በዩክሬንና መካከለኛው ምስራቅ ግጭቶች ዙርያ ተወያዩ

"ሚኒስትሮቹ አንገብጋቢ በሆኑ በርካታ የሁለትዮሽ ጉዳዮች እና የመካከለኛው ምስራቅ እና የዩክሬን ቀውስን ጨምሮ በዓለም አቀፍ አጀንዳዎች ላይ ተወያይተዋል" ሲል የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በሰርጌ ላቭሮቭ እና በባድር አብዴላቲ መካከል ስለተደረገው ውይይት በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

🇱🇧 ላቭሮቭ፤ በሊባኖስ እና በቀጠናው ስላለው ሁኔታ ከቀድሞው የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳድ ሃሪሪ ጋር በአቡ ዳቢ መወያየታቸውንም ሚኒስቴሩ ገልጿል።

ሩሲያ፤ የሊባኖስ ሉዓላዊነት እና አንድነትን ለመደገፍ
አቋሟ የጸና እንደሆነ በድጋሚ አረጋግጣለች ሲልም ሚኒስቴሩ አክሏል።
Via:ስፑትኒክ

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 15:27


#መረጃ‼️ባህርዳር

📌ባህርዳር ኤርፖርት ዛሬ  6:15 አንድ ሄሊኮፕተር በመንደርደር ላይ እያለ ቀላል አደጋ እንዳጋጠመው ተሰምቷል።

📌በዚህ ምክንያት ወደ ባህርዳር የሚደረጉ በረራዎች ተስተጓጉለዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 08:34


በመንግስት የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች ሰላማዊ ዜጎችን ለህልፈት እየዳረገ ነው”- ኢሕአፓ

የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ “የዜጎችን ህይወት የመጠበቅ ሃላፊነት ያለበት መንግሥት ቢሆንም በሚያሰማራቸው የጸጥታ ሃይሎችና የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ጭምር የዜጎች ህይወት በበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች እንደቅጠል እያረገፈ ይገኛል” ብሏል፡፡

ኢሕአፓ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ህገመንግሥቱን የመንግሥት አካላት ራሳቸው ካላከበሩት እንዴት ሊያስከብሩት ይችላሉ “በንጹሀን ዜጎች ላይ የሚደረጉት ግድያዎች ይቁሙ” ሲል አሳስቧል፡፡

እንዲሁም የተለያዩ የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ከመዘገብ ቢቆጠቡም በውጪ የመገናኛ ብዙሀን ጭምር ጥቃቱ መፈጸሙን እየገለጹ መሆኑን እና ፓርቲውም አጣርቻለሁ ያለውን በየክልሉ የደረሱትን ጥቃቶች አስታውቋል፡፡

ፓርቲው አጣርቻለው ባለው መሰረት ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱ ጥቃቶች የሟቾችን ቁጥር እያሻቀበ መሆኑን እና ጥቃት ከተፈጸመባቸው ውስጥም ነፍሰጡሮች፣ የጤና ባለሙያዎች እና በትምህርት ቤት ውስጥ የነበሩ ተማሪዎች እንደሚገኙበት አመላክቷል፡፡

በመሆኑም “ወደፊት ትውልድ እንዲከፍል በብድር በመጣ የጦር መሳሪያ ንጹሀን ዜጎች ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ማካሄድ አግባብነት የለውም”፤ መንግሥት ኃላፊነቱን እየተወጣ ነው ለማለት እንደዚህ ያለውን ሁኔታ በዝምታ ማስቀጠል አይችልም ሲል ኮንኗል፡፡

ኢሕአፓ መንግሥት በተለይ የጦርነት አውድማ በተደረጉት በአማራ፣በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉምዝና በደቡብ ክልሎች ዉስጥ የሚደረገውን ህገመንግሥቱን እየጣሱ ያሉትን፣ መንግሥት መር የዜጎች ግድያዎችን በጥብቅ ማውገዙን እና ጦርነቶቹ አሁኑኑ ይቁሙ ሲልም አሳስቧል፡፡

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 06:58


ታይሰን ተሸነፈ

የ58ዓመቱ አንጋፋ ቦክሰኛ ማይክ ታይሰን በአሜራካዊው ወጣት ተፋላሚ ጃክ ፖል 79 ለ 73 በሆነ ድምር ውጤት ተሸንፏል።

Via HANY NEWS

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 05:50


https://www.tiktok.com/@noralemtube1/photo/7437749767859490104?_r=1&u_code=e0lg2ef75i2ai9&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=ec157e829dkk3d&share_item_id=7437749767859490104&source=h5_m&timestamp=1731736191&user_id=7077185647011152901&sec_user_id=MS4wLjABAAAAeBA_BYMAEd2PX_qli8unwm8BSO2_zQiQ1_eEZzMIzwxqqZP-t_15hZgr0w1rU13O&aweme_type=150&pic_cnt=1&social_share_type=14&ug_photo_idx=0&utm_source=copy&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7434599300442785591&share_link_id=d5abd55d-bb32-4307-b334-ad10c1840ec2&share_app_id=1233&ugbiz_name=UNKNOWN&ug_btm=b8727%2Cb2878&link_reflow_popup_iteration_sharer=%7B%22click_empty_to_play%22%3A1%2C%22dynamic_cover%22%3A1%2C%22follow_to_play_duration%22%3A-1.0%2C%22profile_clickable%22%3A1%7D&enable_checksum=1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 04:34


https://chng.it/zG8yYVkkgp

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 03:59


ከሰሞኑ እንኳን በምስራቅ ጉራጌ ዞን ሶዶ ወረዳ ከ40 በላይ ንፁሀን ዜጎች በግፍ ሲገደሉ፣ በደራ ወረዳ አንድ የመስጂድ ኢማም የሆኑ ሼይህ ከነ12 ቤተሰባቸው ሲረሸኑ፣ ዜጎች በየስፍራው ሲታገቱ እና ወጣቶች በአዲስ አበባ እና አዳማ እየታፈኑ ወደ ካምፕ ዚጓዙ ትንፍሽ ያላለ ሚድያ...

@EliasMeseret

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

16 Nov, 03:29


#አዳማ‼️

ሰዉ ወጥቶ መግባት ቅንጦት ሆኖበታል
ልጆች ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ ወላጆች ተሳቀዋል ፡፡

አፈሳዉ ብሄር ሃይማኖት የትምህርት ደረጃ ሳይለይ በከተማዉ ሁሉም አካባቢ ቀጥሎል ፡፡

የአዳማ ነዋሪዎች የምሬት ድምፅ ነዉ፡፡

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

15 Nov, 17:26


https://www.tiktok.com/@noralemtube1/photo/7437558594754645304?_r=1&u_code=e0lg2ef75i2ai9&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=ec157e829dkk3d&share_item_id=7437558594754645304&source=h5_m&timestamp=1731691573&user_id=7077185647011152901&sec_user_id=MS4wLjABAAAAeBA_BYMAEd2PX_qli8unwm8BSO2_zQiQ1_eEZzMIzwxqqZP-t_15hZgr0w1rU13O&aweme_type=150&pic_cnt=2&social_share_type=14&ug_photo_idx=0&utm_source=telegram&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7434599300442785591&share_link_id=5d7c3054-9ca6-4448-9256-61d665a12a8c&share_app_id=1233&ugbiz_name=UNKNOWN&ug_btm=b2863&link_reflow_popup_iteration_sharer=%7B%22click_empty_to_play%22%3A1%2C%22dynamic_cover%22%3A1%2C%22follow_to_play_duration%22%3A-1.0%2C%22profile_clickable%22%3A1%7D&enable_checksum=1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

15 Nov, 17:03


በኦሮሚያ ክልል የተካሄዱት ሰላማዊ ሰልፎች 'በመንግስት የተመቻቹ ናቸው መባሉን' የክልሉ መንግስት አስተባበለ ‼️

በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖች ትናንት ህዳር 4 ቀን 2017 ዓ/ም የተካሄዱት የሰላም ጥሪ ሰልፎች “በመንግስት የተመቻቹ ናቸው” መባሉን የክልሉ መንግስት “ከእውነት የራቀ” ሲል አስተባበለ።የኦሮሚያ ክልል መንግስት ዛሬ ባወጣው መግለጫ፤ “ህዝቡ ሰላምን ከመጠማቱ የተነሳ የወጣውን ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት አስተባባሪነት እንደተካሄደ ለማሳየት መሞከር ከእውነታ የራቀና የህዝቡን ቁስል በእንጨት መንካት እንደሆነ የሚታሰብ ነው” ብሏል።

መግለጫው የወጣው በክልሉ የተካሄደውን ሰልፍ አስመልክቶ ከመንግስት ጋር ለአመታት የትጥቅ ግጭት በማካሄድ ላይ ያለው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት እና እንደ ጀዋር መሐመድ ያሉ ፖለቲከኞች በመንግስት ላይ ትችት መሰንዘራቸውን ነው።

ፖለቲከኛው ጀዋር መሐመድ በፌስቡት ትስስር ገጻቸው “መንግስት በአንድ በኩል ጉዳዩን የያዙ ሀገሮች ለሶስተኛ ዙር የሰላም ንግግር የሚያደርጉትን ውትወታ ባለመቀበል፤ በሌላ በኩል ምስኪኑን ህዝብ ወደ ፀኃይ በማውጣት ማስወትወት ትክክል አይደለም” ብለዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

15 Nov, 10:47


ፋና ብሮድካስቲንግ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በኦሮሚያ ክልል የታፈሱበት ሰሞንኛ ድርጊት "ሀሰት" መሆኑን ሊነግረን ቀጠሮ ይዟል

ማስረጃዬን ላቀርብ አሰብኩና ለካ እነዚህ ሚድያዎች "ውሸት ነው" ብለው ከዘገቡት "እውነት ነው ማለት ነው" የሚለው ትዝ አለኝ እና ተውኩት።

ቢያንስ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ኮመንት ላይ የሰጡትን አስተያየት አንብቡ። ከተመሠረተ ሶስት ወር እንኳን ያልሞላው መሠረት ሚድያ ከዚህ በተሻለ መረጃዎችን ከነማስረጃቸው ለህዝብ አቅርቧል።

#አትዋሹ #StopFakeNews

@EliasMeseret

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

15 Nov, 10:43


#ቢሊዮን ዶላሮች የሚያወጣ ቢትኮይን የዘረፈው አሜሪካዊ እስር ተፈረደበት ‼️

በዓለማችን እጅግ ግዙፍ ከሚባሉ የክሪፕቶከረንሲ ዝርፊያዎች በአንዱ የተፈፀመውን ገንዘብ አዘዋውሯል የተባለው አሜሪካዊ የአምስት ዓመት እስር ተፈረደበት።ኢልያ ሊክችንስታይን ባለፈው ዓመት ነው ፍርድ ቤት ቀርቦ ጥፋተኛ መሆኑን ያመነው።

ቢትፋይኔክስ የተባለው የክሪፕቶከረንሲ መለዋወጫ መድረክ በአውሮፓውያኑ 2016 ተጠልፎ 120 ሺህ ቢትኮይን መዘረፉ ይታወሳል።ግለሰቡ የተሰረቀውን ክሪፕቶ ያዘዋወረው ከሚስቱ ሄዘር ሞርጋን ጋር ሲሆን የሂፕ ሆፕ ሙዚቀኛዋ ሚስቱ ራዝልኻን በተሰኘ የመድረክ ስሟ ትታወቃለች።ቢትኮይኑ በተሰረቀ ወቅት የገበያ ዋጋው 70 ሚሊዮን ዶላር ነበር። ነገር ግን በቁጥጥር ሥር ሲውሉ ዋጋው ተመንድጎ 4.5 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል።

ግለሰቦቹ በቁጥጥር ሥር ሲውሉ 3.6 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያለው ቢትኮይን ተይዞ ነበር።በወቅቱ ምክትል አቃቤ ሕግ ሊሳ ሞናኮ በአሜሪካ የፍትሕ ሚኒስቴር ታሪክ ይህ ከፍተኛው በቁጥጥር ሥር የዋለ ገንዘብ ነው ማለታቸው አይዘነጋም።

“እንዲህ ዓይነት ወንጀል ፈፅመው ሳይቀጡ እንደማያልፉ ማሳያ ነው። የሚፈፅሙት እያንዳንዱ ወንጀል መዘዝ አለው” ሲሉ ዳኛ ኮሊን ኮላር-ኮቴሊ ተናግረዋል።ሊክችንስታይን በአውሮፓውያኑ የካቲት 2022 ነው በቁጥጥር ሥር ውሎ እስር ቤት የገባው።ሰውዬው በፈፀመው ወንጀል መፀፀቱን ለችሎቱ ተናግሯል።

አክሎ እስሩን ጨርሶ ሲወጣ ችሎታውን ተጠቅሞ የሳይበር ወንጀለኞችን ለመከላከል እንደሚሠራ ቃል ገብቷል።ሚስቱ ሞርጋን በገንዘብ ማዘዋወር ውስጥ እጇ እንዳለበት አምና ጥፋተኛ ነው ያለችው ባለፈው ዓመት ነው። በሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ ፍርድ ቤት ቀርቦ ብይን ይሰጣታል ተብሎ ይጠበቃል።

Via BBC

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

15 Nov, 08:44


#ኢትዮጵያ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙርያ በተሰጠ አስተያየት ምክንያት የሱዳን አምባሳደርን ጠራች‼️

የሱዳን ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት አሊ የሱፍ "በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ ውሳኔ ያላገኙ እና ያልተፈቱ ልዩነቶች ወደ ጦርነት ሊያመሩ ይችላሉ" ሲሉ የሰጡትን አስተያየት ተከትሎ ኢትዮጵያ የሱዳንን አምባሳደር ረቡዕ ዕለት ጠርታ ማነጋገሯን ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል።

ሚንስትሩ በቅርቡ በቴሌቭዥን ቀርበው ባደረጉት ቃለ ምልልስ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙርያ የሚደረጉ ድርድሮች የማይሳኩ ከሆነ ሱዳን ከ #ግብፅ ጋር ልትሰለፍ እንደምትችል ገልፀው ጦርነት የሶስቱንም ሀገራት የውሃ ተጠቃሚነት መብት የሚያረጋግጥ አማራጭ መሆኑን አስታውቀዋል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሱዳን አምባሳደር አልዘይን ኢብራሂም ጋር ባደረገው ውይይት በጉዳዩ ደስ አለመሰኘቱን ገልጾ በሁለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት መግለጻቸውን ዘገባው አመልክቷል።

የሱዳን ጊዜያዊ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት አሊ የሱፍ በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ ሊሰጡ በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ ሊመጡ እንደሚችሉ የዲፕሎማቲክ ምንጮች ጠቁመዋል ተብሏል። 

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ የሆኑት አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ትናንት ህዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር ያላትን “የዳበረ እና ስትራቴጂካዊ” ግንኙነት በመጥቀስ የህዳሴ ግድብ ጉዳይን በውይይት ለመፍታት ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።

አክለውም ኢትዮጵያ ላለፉት 13 ዓመታት ካካበተችው ልምድ ግድቡ በታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ላይ ጉዳት እንደሌለው የሚያረጋግጥ መሆኑንና ይልቁኑ ቀጠናዊ ትብብርን እንደሚያጠናክር አጽንኦት ሰጥተዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 15:49


#አመራሩ ተገደሉ‼️

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን የቆቦ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ የነበሩት ደርቤ በለጠ ዛሬ ረፋድ ላይ በተተኮሰባቸው ጥይት ህይወታቸው ማለፉን የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል።
Via:አዩ
ነፍስ ይማር

⬇️⬇️⬇️⬇️👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 15:47


https://vm.tiktok.com/ZMhb7HbtY/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 15:39


<< በጭንቀት ላይ ለሰነበታችሁ ዘመድ ወዳጆቸ እና የትግል አጋሮቸ በሙሉ።

ለገጠመኝ የጤና ችግር ከአንድ ቀን በፊት የተካሄደልኝ የቀዶ ጥገና ህክምና በጥሩ ሁኔታ ተጠናቋል። የፈጣሪ ፈቃድ ሆኖ አሁን ላይ ጤናየ በጥሩ ሁኔታ ስለሚገኝም ከሆስፒታል ወጥቸ ወደ ቤቴ ተመልሻለሁ። ስለ ደህንነቴ ተጨንቃችሁ በፀሎትና በሀሳብ ስታግዙኝ ለሰነበታችሁ ወዳጅ ዘመዶቸ በሙሉ ልባዊ ምስጋናየን አቀርባለሁ። አሁን ረዥም ጊዜ የፈጀው የህክምናየ ሂደት በመጠናቀቅ ላይ ነው። ስለሆነም ወደ አገሬ ተመልሸ ለመሄድ የነበረኝ ከፍተኛ ፍላጐትና ጉጉት ዕውን ሊሆን በመቃረቡ ደስ ብሎኛል።>>

ከአክብሮት ጋር
ልደቱ አያሌው
ህዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 15:38


መንግስት በአማራ ባለሀብቶች በኩል "አመቻች ኮሚቴ" የሚል ስያሜ የተሰጠው የባለሐብቶች ስብስብ አዋቀረ ‼️

ይህ አመቻች ኮሚቴ የተባለው የአማራ ባለሀብቶች ስብስብ የተመረጠው ጥቅምት 21/ 2017 ዓ.ም ባህርዳር ከተማ በሚገኘው ብሉ ናይል አቫንቲ ሆቴል በተደረገ ስብሰባ መሆኑ ታውቋል።

ሰብሳቢዎቹ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አረጋ ከበደ፣ የባህር ዳር ከተማ ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳለው እና የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግሥቴ መሆናቸው የተረጋገጠ ሲሆን በዚህ መድረክ ላይ አመቻች ተብለው የተመለመሉት ባለሐብቶች እና ሌሎች ግለሰቦች አቶ በላይነህ ክንዴ፣ አቶ ካሳሁን ምስጋናው፣ አቶ ታደሰ ምህረቴ፣ አቶ ሙሉጌታ ቢያዝን፣ ዶ/ር መኮንን አይችሉህም፣ አቶ ፀጋ አስማረ፣ አቶ ወርቁ ታምራት፣ ኢንጂነር ጌታሁን ሁሴን እና ወ/ሮ ቃልኪዳን ጠብቀው እንደሆኑ ሰምተናል።

የተጠቀሱት የግለሰቦች ስብስብ በሰላም አመቻችነት ከተሰየሙ በኋላ በመንግስት ከፍተኛ አመራሮች በቀጣዩ ቀን ተሰብስበው በክልሉ ባለው ግጭት ዙርያ ምን መሰራት እንዳለባቸው እንደተነገራቸው ተሰምቷል።

መንግስት በሰሜኑ ጦርነት ወቅትም የትግራይ ባለሀብቶችን በመሰብሰብ ተመሳሳይ ሙከራ ሲያደርግ እንደነበር ይታወሳል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 13:49


#ትግራይ

" ቡድኑ ለስልጣን ሲል ማንኛውም ዓይነት ጥፋት ከመፈፀም ወደ ኋላ እንደማይል በተደጋጋሚ እየታየ ነው " - የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር

የትግራይ ጊዚያዊ አስተደደር ዛሬ ህዳር 1/2017 ዓ.ም የፅሁፍ መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም " በአንደኛው ገፅ ልዩነቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተካረሩ ሄደዋል በሌላኛው ገፅ ደግሞ የጊዚያዊ አስተዳደሩ እቅዶች የማደናቀፍ እና የማዳከም የተቀናጀ ዘመቻ ሲደረግ ቆይቷል አሁንም ቀጥሏል " ሲል ገልጿል።

በተለይም ከነሀሴ 2016 ዓ/ም ጀምሮ በህወሓት ከፍተኛ አመራሮች መካከል የተፈጠረው አለመግባባት እና በግልፅ የታየው ልዪነት መሰረታዊ የህዝብ ጥያቄያዎች በተቀናጀ መልኩ እንዳይፈቱ ከባድ እንቅፋት ፈጥረዋል ብሏል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩን እቅዶች በተቀናጀ መልኩ የሚያደናቅፈው ህጋዊ ያልሆነ ጉባኤ ያካሄደው ቡድን ከፍተኛ አመራር ነው ያለው ጊዜያዊ አስተዳደሩ " ደርጊቱ ህዝቡ ተስፋ እንዲቆርጥ ሆነ ተብሎ የሚደረግ ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው " ሲል አውግዞታል። 

" የቡድኑ ተግባር የጊዚያዊ አስተዳደሩ እቅዶች ከማደናቀፍ በዘለለ ይፋዊ ወደ ሆነ የመንግስት ግልበጣ እና ስርዓት አልበኝነት ማስስፋፋት ከፍ ብሏል " ሲል ከሷል።

ከቅርብ ጊዚያት ወዲህ በመቐለ ከተማ  ፣ በሰሜናዊ እና ማእከላዊ ዞኖች የታዩት የመንግስት ግልበጣና ስርዓት አልበኝነት ምልክቶች የቡድኑ ህግ አልበኝነት ማሳያ ናቸው ሲል አስረድቷል።

" ቡድኑ በአሁኑ ሰዓት ደግሞ የመንግስት የአመራር እርከን ከላይ እስከ ታች ለመቆጣጠር ጨርሰናል " የሚል የማደናገሪያ እቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ እንደሆነ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል።

" የቡድኑ ማደናገሪያ በአጉል ተስፋ ራስን ከማታለል የዘለለ ቅንጣት ሀቅ እንደሌለው መታወቅ አለበት " ያለው አስተዳደሩ " ቡድኑ ለስልጣን ሲል ማንኛውም ዓይነት ጥፋት ከመፈፀም ወደ ኋላ እንደማይል በተደጋጋሚ እየታየ መጥቷል " ሲል ገልጿል።

" ' ከሰራዊት አመራሮች ተግባብተናል ' በሚል እየነዛው ያለው ማደናገሪያ ለጠባብ የስልጣን ፍላጎቱ ማሟያ ነው " ብሏል።

" በትግራይ ህልውና የቆመው ሃይል ከመጠቀም እንደማይመለስም ማሳያ ነው " ሲል አክሏል።

" ቡድን " ሲል የገለፀው አካል በሃይማኖት አባቶች የተጀመረው ነገሮች በውይይት የመፍታት ሂደት እንደማይቀበል በአደባባይ ገልፀዋልም ሲል ጊዜያዊ አስተዳደሩ ገልጿል።

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮቼ አሁንም ነገሮች በሰከነ አኳሃን በሰላም እና በውይይት ለመፍታት ዝግጁ ናቸው ብሏል።

የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራሮች የጀመሩት የሰላምና የውይይት ጥረት እንዲሳካ ሁሉም ከጎኑ እንዲሰለፍ ጥሪ አቅርቧል።

በቅርቡ የትግራይ ሃይማኖት አባቶች የህወሓት አመራሮች በመካከላቸው ያለውን ልዩነት በንግግር እንዲፈቱ ለማድረግ ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል እና አቶ ጌታቸው ረዳ እና አመራሮቻቸውን በአካል አገናኝተው ነበር።

ከዚህ መድረክ በኃላ በወጡ የተለያዩ ፎቶዎች በርካቶች " ችግሩ በንግግር ሊፈታ ነው " በሚል ብዙ ተስፋ አድርገው ነበር።

በደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራው ህወሓት ትናንት በትግራይ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት አባቶች አማካኝነት ሁለቱ የህወሓት ቡድኖች ያደረጉት የፊት ለፊት ግንኙነት ከብፁአን የሃይማኖት አባቶች ተግሳፅና ምክር የዘለለ ውጤት እንደሌለው ተናገረ።

የደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት ዛሬ ምሽት አጭር መግለጫ አውጥቷል።

አንዳንድ ሚዲያዎች ደግሞ " ለእርቅና ሽምግልና ተስማምተዋል " የሚል መረጃ እስከማሰራጨትም ደርሰው ነበር።

በኃላ በዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል የሚመራው ህወሓት ፥ " በብፁአን አበው የተዘጋጀው ፊት ለፊት የማገናኘት መርሃ ግብር ልዩነቶች በህግ ፣ ተቋማዊ ስርዓት ማእከል በማድረግ ህዝብን ከአደጋ መታደግ በሚችል የሰለጠነ ሰላማዊ መንገድ ችግሮቻችን እንድንፈታ ያለመ የምክርና የተግሳፅ መድረክ ነበር " ሲል አሳውዋል።

" ብፁአን አበው ላቀረቡልን ምክርና ተግሳፅ ያለንን ክብርና ድጋፍ ገልፀናል ፤ ከዚህ በዘለለ የተለያዩ አካላትና ሚዲያዎች ' ለእርቅ እና ሽምግልና ተስማምተዋል ' በማለት የሚያሰራጩት መረጃ ከእውነት የራቀ ነው " ሲል ነበር የገለጸው።

በቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ተዘጋጅቶ የተላከ።

#TikvahEthiopiaFamilyAA #Tigray #Mekelle

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 13:10


ከሰሞኑ ወደ ኢትዮጵያ 'ስውር' በረራ ያደረጉ የውጭ ሀገራት ምዝገባ ያላቸው አውሮፕላኖች ጉዳይ‼️

አንደኛው በረራ ሩስያ ስሪት በሆኑ ኢልዩሽን አውሮፕላኖች ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ወደ አዲስ አበባ የተደረጉ ተደጋጋሚ በረራዎች ናቸው።

እነዚህ ኢልዩሽን IL-76 አውሮፕላኖች ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ የራዳር ስማቸው በማጥፋት የተከናወኑ ሲሆን ወደ ኤምሬትስ ሲመለሱ ደግሞ ሌላ ስያሜ እንደተጠቀሙ ታውቋል።

አውሮፕላኖቹ ከኤምሬትስ ይነሱ እንጂ የተመዘገቡት ኪርጊዝታን መሆኑን ምንጮቻችን ጨምረው ገልፀዋል። አውሮፕላኖቹ ብዙ ግዜ የጦር መሳርያ በማመላለስ ይታወቃሉ።

ሌላኛው ስውር በረራ ደግሞ ባሳለፍነው ማክሰኞ የተከናወነ ሲሆን ፎኔክስ ኤር የተባለ የኪራይ የግል ጄት ከግሪክ ተነስቶ አዲስ አበባ ካረፈ በኋላ ከ90 ደቂቃ በኋላ ተመልሶ ወደመጣበት እንደሄደ ታውቋል።

ይህን አውሮፕላን ዘወትር የሚከራዩት የአሜሪካው CIA ሀላፊዎች ሲሆኑ በማክሰኞው በረራ ማንን ይዞ እንደነበር ግን አልታወቀም።

የሲአይኤው ሀላዊ ዊልያም በርንስ በቅርቡ በኬንያ እና ሱማልያ በመገኘት መሪዎችን ሲያናግሩ እንደነበር ይታወሳል።

ባለስልጣኑ ምናልባት በዚህኛው የአዲስ አበባ በረራ አዲስ አበባ ተገኝተው የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናትን በስውር አግኝተው ተመልሰው ሊሆን ይችላል የሚል ግምት እንዳለ ለሚድያችን የደረሰው ጥቆማ ያሳያል።
#MeseretMedia
👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 13:09


#Bankology ‼️

የባንክ ኢንዱስትሪውን ዘግይተው ከተቀላቀሉ መካከል አንዱ የሆነዉ አሃዱ ባንክ በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት ከታክስ በፊት 120 ሚሊዮን ብር ገደማ ትርፍ ማግኘቱን ገልጿል።

ባንኩ ስራ በጀመረበት የመጀመሪያ አመት ማለትም 2015 የስራ አፈፃፀሙ 267.7 ሚሊዮን ብር ኪሳራ ያስመዘገበ ቢሆንም በተያዘው በጀት ዓመት ግን ወደ ትርፍ መሸጋገር መቻሉን ነዉ በሪፖርቱ ያስታወቀው።

በሁለት ዓመቱ የስራ ቆይታዉ ትርፍ ማስመዝገብ የቻለዉ አሃዱ ባንክ አጠቃላይ ሃብቱ 6.4 ቢሊዮን ብር መድረሱን እና 1.4 ቢሊዮን ብር ደግሞ የተፈረመ ካፒታል መሆኑን ጠቅሷል።

እኤአ በ 2021 የተቋቋመው ባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ሂሳብ 4.66 ቢሊዮን ብር መድረሱን ገልጿል። በተጠቀሰው የስራ ዘመን 80 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚሆን የዉጭ ምንዛሪ መሰብሰብ መቻሉን ነዉ ያስታወቀው።

Via Capital

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

10 Nov, 13:07


ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የመቄዶንያ ብራንድ አምባሳደር ሆነ!

በሀይማኖታዊ አስተምሮቶቹ የሚታወቀውናአመለ ሸጋዉና አንደበተ ርቱዕ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ የመቄዶንያ የአረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ የበጎ ፈቃድ ብራንድ አምባሳደር በመሆን የስምምነት ፊርማ ስነስርዓት ዛሬ ጥቅምት 30/02/2017ዓ.ም. ከረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ በመቄዶኒያ የአረጋዊያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማህበር ሐያት በሚገኘዉ በዋናው ግቢ ውስጥ (መቄዶንያ) ታላቁ ዝግጅት ተከናዉኗል!

ማዕከሉ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌን የመቄዶንያ የበጎ ፈቃድ አምባሳደር አድርጎ በበጎ ፈቃድ ስራዎች ላይ ሰፊ ስራ እንዲሰሩ ሀላፊነት የሰጠ መሆኑን መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ተገኝተን ተመልክተናል!

ዲ/ን ሄኖክ በሜቄዶንያ አምባሳደርነቱ ማእከሉን በመወከል ፣ በማስተዋወቅ ፣ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራሞች ላይ በመሳተፍ የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ገልጿል።

" መቄዶንያ ተሳልመን ባንገባም የተቀደሰ ስፍራ ነው ። ይህን ማዕከል ለማገልገል መመረጥ ለኔ ክብር ነው " በማለትም ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ተናግሯል ።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ባዚልያድ የተሰኘዉን አዲስ መፅሐፍ ምረቃና መሉ የመፅሐፉ መፅሐፉን ሽያጭ ገቢ ለመቄዶንያ እንዲሆን በይፋ አበርክቷል!

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

09 Nov, 16:36


https://vm.tiktok.com/ZMhbhABNY/

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

09 Nov, 16:11


https://t.me/PAWSOG_bot/PAWS?startapp=0RklOX8e
LFG!
PAWS is the new top dog! 🐾

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

09 Nov, 15:40


የኢትዮጵያ አየር ሀይል ዋና አዛዥ የሆኑት ሌተናል ጄነራል ይልማ ከትዊተር (ኤክስ) መተግበርያ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንደታገዱ ለማወቅ ችለናል።

እንዲህ አይነቱ ክስተት የሚፈጠረው የሀሰተኛ የጥላቻ ንግግሮችን በሚያሰራጩ ሰዎች ላይ ነው።
ጀነራሉ ወደፊትም በስማቸው የX አካውንት እንዳይከፍቱ ጭምር ነው እግዱ።


https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

09 Nov, 14:16


በኦሮምያ ክልል ነዋሪዎች ለተማሪዎች ምገባ ፕሮግራም እና ለሚሊሻዎች በሚል አስገዳጅ መዋጮ እየተጠየቁ መሆኑን አስታወቁ ‼️

የኦሮምያ ክልል ነዋሪዎች የአከባቢው ባለስልጣናት በግዳጅ ለተማሪዎች የምገባ ፕሮግራም እና የአከባቢውን ሚሊሻዎች ለማጠናከር በሚል መዋጮ በተደጋጋሚ አንደሚጠየቁ አስታወቁ።

በተለያዩ መክንያቶች ባለስለጣናቱ አስገዳጅ መዋጮዎችን ስለሚያስከፍሏቸው ለከፍተኛ የገንዘብ ችግር እየተዳረጉ መሆኑን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፣ ለኑሮ ጫና ዳርጎናል ብለዋል።

ባለስልጣናቱ መዋጮ እንዲከፍሉ የሚያስገድዱት መንግስት ሰራተኞችን እና የየአከባቢዎቹን አርሶአደሮች ጨምሮ ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል መሆኑን ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል።

በምዕራብ አርሲ ዞን የቆፋሌ ወረዳ ነዋሪ የሆኑ እና ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አርሶ አደር እንዳስታወቁት ከአምና 2016 ጥር ወር ጀምሮ ነዋሪዎች ለተማሪዎች ምግብ፣ ለሚሊሻ ዩኒፎርም እና ለምግብ አቅርቦት የሚሆን ገንዘብ እንዲያዋጡ እንደሚጠየቁ አስታውሰዋል።

በተመሳሳይ በኦሮሚያ ክልል ሻሸመኔ ከተማ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህር የሆኑት ተስፋዬ ቶሎሳ (ስማቸው የተቀየረ) ከወርሃዊ ደመወዛቸው 6ሺ ብር ላይ ምክንያቱ ሳይገለጽላቸው እየተቀነሰባቸው መሆኑን ገልጸው እጅግ አሳስቦኛል ሲሉ አስታውቀዋል።
Via -adisstandard

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

03 Nov, 12:53


#CBE ‼️

የኢትዮጵያ ንግድ በባለፈው መጋቢት ወር 2016 ዓ.ም በሲስተም ችግር ምክንያት ተዘርፎ ከነበረው ገንዘብ ውስጥ ማስመለስ ያልቻለውን የባንኩ ሰራተኞች እንዲከፍሉ ማድረጉ ተሰምቷል።
ባሳለፍነው ሳምንት ረቡዕ አንዳንድ የባንክ ቅርንጫፍ ስራአስኪያጆች ሰራተኞቻቸውን ሰብስበው ያልተመለሰውን ቀሪውን ገንዘብ ሰራተኞቹ እንዲከፍሉ መወሰኑ የተሰማ ሲሆን እያንዳንዱ የባንክ ሰራተኛ ካሳለፍነው ሳምንት ሀሙስ ጀምሮ በነፍስ ወከፍ ቢያንስ 1000 ብር እንዲከፍሉ ማስደረጉን ሰምተናል። ለአብነት
ቢላ ቅርንጫፍ ፣ አየር አምባ ቅርንጫፍ ቦሌ ሚካኤል ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጆች ከማኔጅመንቱ ደብዳቤ የደረሳቸው ሲሆን የተወሰነው ገንዘብ ተዋጥቶ ካልተመለሰ ስራአስኪያጆቹ እንደሚሰናበቱ ተነግሯቸዋል ብለውኛል።
ባንኩ በወቅቱ ተዘርፎበት ከነበረው ገንዘብ ውስጥ 98% አስመልሻለሁ ማለቱ ይታወሳል።

👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

03 Nov, 12:27


በደረሰው የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር ከ200 ማለፉ ተነገረ

በደቡብ ምስራቅ ስፔን ቫሌንሺያ ከተማ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በርካታ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ እና ከፍተኛ ንብረት መውደሙ ተገልጿል።

የጎርፍ አደጋውን ተመልክቶ የሚወጡ ምስሎች እና ቪድዮዎችም የአደጋውን አስከፊነት የሚያመለክቱ ሆነዋል።

የሀገሪቱ ምስራቃዊ ግዛት በሆነችው ቫሌንሺያ የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ በትንሹ ከ200 በላይ ሰዎችን ህይወት መቅጠፉ ተጠቅሷል።

የነብስ አድን ሰራተኞች አሁንም በጎርፉ ምክንያት የጠፉ ሰዎችን የማፈላለጉን ስራ አጠናክረው መቀጠላቸውን የዘገበው ሞርኒግ ፖስት ነው።(Getu)

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

03 Nov, 05:16


#አለም ከአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ተፅእኖ ላይ ላለመውደቅ አዲስ ሐይማኖት ያስፈልገዋል _ቢል ጌትስ

ቱጃሩ የማይክሮሶፍት  መስራች ቢልጌትስ ከግራ ዘመሙ ቢልየነር ሬድ ሆፍማን ጋር ሰሞኑ ባደረጉት የፖድካስት ውይይት ላይ እንደተናገሩት
"አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ብዙ ነገር እየተቆጣጠረ ነው በዚህም ሰዎች ለወደፊት ብዙ ስራ ላይሰሩ ይችላሉ።

ብዙ ጊዜያቸውን በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ  ክንዋኔች ላይ በማዋል የገሀዱን  አለም ሊረሱ ይችላሉ። ስለዚህ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ባህሪያቸውን ቀይሮ ብዙ ነገራቸውን እንዳያበላሽ አዲስ ሐይማኖት ወይም ፍልስፍና ያስፈልጋቸዋል ባይ ነኝ "ሲሉ ተደምጠዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

03 Nov, 04:01


#Update #Earthquake

በዓለም አቀፍ ደረጃ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶችን የሚከታተለው የ ' የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ / USGS ድረገጽ ' ከአዋሽ 29 ኪ/ሜ ርቀት ላይ ዛሬ ሌሊት 6:04 በሬክተር ስኬል 4.7 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ገልጿል።

ትላንትና ለሊት ላይ የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.6 ነበር የተመዘገበው ፤ የዛሬው 4.7 ነው የተመዘገበው።

Via:tikvah

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

03 Nov, 03:58


#ባለሃብቱ ሸህ አሊ ሁሴን መታሰራቸው ተሰምቷል።

ሸህ አሊ የአልፎዝ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ባለቤት ሲሆኑ አቢሲኒያን ጨምሮ የበርካታ ባንኮች ከፍተኛ ባለሸር ናቸው ተብሏል።

ባለሃብቱ በምን ጉዳይ ተጠርጥረው እንደተያዙ ባይታወቅም ዛሬ ጥቅምት 19/2017 በፖሊስ መያዛቸው ታውቋል።

ሸህ አሊ አልፎዝ ፕላዛን ጨምሮ በርካታ በቤተሰብ የሚመሩ ድርጅቶች ባለቤት መሆናቸው ታውቋል።

በቅርቡ ሌላኛው ታዋቂ ባለሃብት አቶ መቅደስ አክሊሉ መታሰራቸው ይታወሳል።

ቤተሰብ
አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

02 Nov, 14:11


#የፋኖ አመራሮችን ኢላማ ያደረገ የድሮን ጥቃት መፈፀሙ ታወቀ

"በመግለጫ፤ በመልዕክት እና በፎቶ ጋጋታ ህዝብን መሸወድ አይቻልም" የሚሉ ፅሁፎች ባለፉት ጥቂት ቀናት ማህበራዊ ሚድያ ላይ በስፋት የተሰራጩ ሲሆን በይዘታቸውም የፋኖ አመራር የሆነው ዘመነ ካሴ በድሮን ጥቃት እንደተገደለ ይገልፃሉ።

"የሞተ ሰው መቼም አይነሳም፣ ዘመነ በህይወት ቢኖር መቼም በሚዲያ ወጥቶ ባልዋለበት አውደ ውጊያ እንደዋለ አድርጎ የሚያወራ ሰው አሁን በድምጽ ፊት ለፊት መግለጫ መስጠት አይቻልም" የሚሉት እነዚህ ፅሁፎች ለዘመነ መሞት አስረስ ማረ ዳምጤ በተደጋጋሚ የዘመነ መልዕክት በሚል የሚያወጣቸውን ፎቶዎች በማስረጃነት ሲያቀርቡ ተመልክተናል።

በዚህ ዙርያ መሠረት ሚድያ ማጣራት ያደረገ ሲሆን አየር ሀይል የፋኖ አመራሮችን ኢላማ ያደረገ ተደጋጋሚ ጥቃት ባሳለፍነው ሳምንት ማድረጉን አረጋግጧል።

"እኔም የጥቃቱ ኢላማ ነበርኩ" ብሎ ቃሉን ለመሠረት ሚድያ የሰጠው የፋኖ ሀይሎች የፖለቲካ ዘርፍ ሀላፊ አቶ አስረስ ማረ ዳምጤ የድሮን ጥቃቱ አሁን አሁን የየእለት ድርጊት ሆኗል ብሏል።

አስረስ ማረ ስለ ዘመነ ካሴ ማህበራዊ ሚድያ ላይ የሚዘዋወረውን መረጃ በተመለከተ ለቀረበለት ጥያቄ ሲመልስ "ሁላችንም ሰላም ነን" በማለት መረጃው ትክክል እንዳልሆነ ጠቁሟል።

አክሎም "የድሮን ጥቃቱ እስካሁን ለዘመነ ስጋት አልነበረም፣ ይሁንና በቅርቡ እርሱ የነበረባቸው 3 ቦታዎች በድሮን ተመተዋል። ጥቃቱ እሱን ሳይሆን ንፁሀን ዜጎችን ሰለባ አድርጓል" በማለት ተናግሯል። 
via_መሰረት ሚድያ

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

02 Nov, 11:09


#5𝗲𝘁𝗯 የአምስት ብር ኖት የመግዛት አቅም በመቀነሱ ወደ ሳንቲምነት ሊቀየር መሆኑ ተሰምቷል።
ከዚህ በፊት የወረቀቱ አንድ ብር ወደ ሳንቲም መቀየሩ ይታወሳል።ከአምስት ብር ቀጥሎ ተረኛው አስር ብር ሊሆን እንደሚችል ምንጮች ጨምረው ገልፀዋል።

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

02 Nov, 11:07


#አዳማ‼️
በአዳማ ከተማ ሰሞኑን ዘመቻ በሚመስል መልኩ ወጣቶች እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተወሰዱ መሆኑን የደረሰኝ መረጃ ያመላክታል።
👉ይሄን ፈርተን በጊዜ ነው ወደ ቤታችን የምንገባው ብለዋል።
ግማሾቹን ብር እያስከፈሉ ይለቋቸዋል፣ብር የሌላቸውን ወደየት እንደሚወስዷቸው አይታወቅም ብለዋል።
ብዙ ወጣቶች ከ25,000 ብር እስከ 50,000 ብር እየከፈሉ እንደተለቀቁና እኔም 25,000 ብር ከፍዬ ነው የወጣሁት ሲል አንድ የአዩዘሀበሻ አባል ገልጿል።
ይሄን የሚፈፅሙት በከተማዋ የሚንቀሳቀሱ ሚሊሻዎች ናቸው ብለዋል።
ትናንት ብቻ በከተዋ ከሚገኝ አንድ ፋብሪካ 10 የፋብሪካው ሰራተኞች በፀጥታ አካላት ተይዘው ተወስደዋል ብለዋል።
Via:አዩ
👇👇👇👇👇👇👇👇⬇️
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇👇

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

02 Nov, 11:05


አቶ ጌታቸው ረዳ ኃላፊነታቸውን ማስረከባቸው ተሠማ

አቶ ጌታቸው ረዳ ኃላፊነታቸውን ያስረከቡት ለምክትላቸው ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ በውክልና መሆኑ ታውቋል።

አቶ ጌታቸው ለህክምና ወደ ውጭ ሊሄዱ በመሆኑ ነው ስልጣናቸውን በውክልና ያስተላለፉት ተብሏል።

ሌተናል ጀኔራል ታደሰ ወረደ የትግራይን የፀጥታ ኃይል ከመምራታቸው በተጨማሪ የእነ ደብረፂዮን ህውሃት ደጋፊ መሆናቸው ይነገራል።
Via_degu

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

02 Nov, 10:32


#የመምህራን ምገባ መርሐግብር

በሸገር ከተማ አስተዳደር በሁሉም የመንግስት ቅድመ መደበኛ እና አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተማሪና መምህራን የምግብ ፕሮግራም በመተግበር ላይ ይገኛል።

በዚህ ፕሮግራም የተማሪዎች ትምህርት ማቋረጥን ማስወገድ የተቻለ ሲሆን መምህራንም በማስተማር እና በመማር የበለጠ እንዲተጉ አድርጓል ተብላል።

በሸገር ከተማ በሚገኙ 256 ትምህርት ቤቶች የተማሪ እና የመምህራን  ምግብ ፕሮግራም እየተካሄደ ሲሆን እስካሁን ለ148 ሺ 795 ተማሪዎች እና ለ3 ሺ 707 መምህራን መስጠት ተችሏል።(የኔታ ቲዩብ)

አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

02 Nov, 10:31


#ከሞት ፍርዱ በፊት  "ሲጃራ ላጭስ ሲል " የወህኔ ቤት ሀኪሞች " ለጤናክ ይጎዳካል " ተብሎ የነበረው አሜሪካዊው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል

ሰሞኑ የአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን በሞት ፍርድ ከ30 አመት በፊት የሞተውን ኢንግራምን ጉዳይ ይዘው ወጥተው ነበር።
ኢኒግራም የዛሬ 42 ዓመት ሰው ቤት ገበቶ ባልን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ ሚስትን ደግሞ አቁስሎ 60 ዶላር ሰርቆ የሄደ ቢሆንም በፖሊስ ተይዞ የዛሬ 30 በኤሌትሪክ ሽቦ ታስሮ የሞት ፍርድ ተፈፅሞበታል።

ጉዳዩን እንዲነሳ ያደረገው የኢኒንግራም ጠበቃ የነበረው ክላይቭ ስታፎርድ ስሚዝ ደንበኛው የሞት ፍርድ ከመፈፀሙ በፊት ምግብ እንዲቀርበለት ሲጠየቅ "አይ ሲጃራ አምጡልኝና ላጭስ "ሲል የወህኔ ቤቱ ሀኪሞች "አይ ሲጃራ ለጤናክ ጉዳት አለው "በማለት ሲጃራ እንደከለከሉትና ከሰአታት በኋላ  የኤሌትሪክ ሽቦ ባለው ወንበር ላይ የሞት ፍርዱ እንደተፈፀመበት ሰሞኑን ተናግሯል።

ጠበቃው የሞት ፍርዱ ሊፈፀም የቀረበ ሰው "ሲጃራ ለጤናክ  ይጎዳካል ማለት ቀልድ ነው ወይስ ፌዝ "በማለት የወህኔ ቤቱ አስተዳደር የመብት ጥሰት እንደፈፀመ አስረድቷል።( ጥንቅር fidel post)

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

02 Nov, 04:11


🚩የአሜሪካ 🇺🇲 ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለምን ማክሰኞ ዕለት ብቻ ይካሄዳል?


የዓለማችን ልዕለ ሀያል ሀገር አሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ሊካሄድ አምስት ቀናት ብቻ ቀርቶታል።
በሪፐብሊካኑ ዶናልድ ትራምፕ እና ዲሞክራቷ ካማላ ሀሪስ መካከል የሚካሄደው ይህ ምርጫ የፊታችን ማክሰኞ ይካሄዳል።
አሜሪካ በየ አራት ዓመቱ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት፣ ምክትል ፕሬዝዳንት እና ህግ አውጪ ምክር ቤት አባላት ምርጫን አንዴ ታካሂዳለች።
ይህ ምርጫ ከፈረንጆቹ 1845 ጀምሮ በመካሄድ ላይ ሲሆን ምርጫው ሁልጊዜ ማክሰኞ ዕለት ብቻ ይካሄዳል።
ምርጫው የሚካሄድበት ሕዳር ወር እና ማክሰኞ ዕለት እንዲሆን የተመረጠው ደግሞ የምርጫ ማስፈጸሚያ ህጉ በወጣበት ጊዜ በአብዛኛው የአሜሪካ አካባቢዎች ማክሰኞ ዕለት ገበያ ስላለ እና ህዝቡ በአንጻራዊነት እረፍት የሚያደርግበት ዕለት ነው በሚል እሳቤ ነበር።
በአብዛኛው የዓለማችን ሀገራት ምርጫዎች የሚካሄዱት ዕሁድ ዕለት ሲሆን በአሜሪካ ይህ ዕለት የድምጽ መስጫ ቀን ያልተደረገው በወቅቱ አብዛኛው አሜሪካዊ ዕሁድ ዕለትን ለአምልኮ ብቻ የማዋል ልምድ ስለነበረው እንደሆነበኖርዝ ኢስተርን ዩንቨርስቲ የታሪክ ፕሮፌሰር የሆኑት ጀሲካ ሊንከር ተናግረዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ሕዳር ወር ድምጽ የሚሰጥበት ወር ሆኖ የተመረጠው አብዛኛው አሜሪካዊ ይህን ወቅት ሰብሉን አስቀድሞ ስለሚሰበስብ እና ያገሬው ገበሬ የተሻለ የዕረፍትጊዜ የሚያገኝበት ወቅት ስለሆነ ነበር።
አሜሪካዊያን አሁን ያለው ህይወት የምርጫ ህጉ ከወጣበት ጊዜ ሲነጻጸር በብዙ መልኩ ለውጥ ያለ ቢሆንም የሀገሪቱን ታሪክ ላለማጥፋት ሲባል ህጉ ባለበት እንዲቀጥል ተደርጓል።
በዘንድሮው ምርጫ ላይ ዋነኛ ተፎካካሪ የሆኑት ዶናልድ ትራምፕ እና ካማላ ሀሪስ ፉክክሩን የቀጠሉ ሲሆን ታዋቂ ሰዎች እና ተጽዕኖ ፈጣሪዎችም በምረጡኝ ቅስቀሳው ላይ እየተሳተፉ ናቸው።
የዓለማችን ቁጥር አንድ ባለጸጋ ኢለን መስክ የዶናልድ ትራምፕ ደጋፊ ሲሆኑ እንደ ቴይለር ስዊፍት፣ ቢዮንሴ እና ሊኦናርዶ ዲካፕሪዮ ደግሞ የካማላ ሀሪስ ደጋፊ መሆናቸውን በይፋ አውጀዋል።

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

26 Oct, 16:53


ከ56 በመቶ በላይ ኢትዮጵያዊያን ሀገራቸዉ በትክክለኛው ሀዲድ ላይ አለመሆኗን ያምናሉ ሲል አንድ ጥናት ያመላከተ ሲሆን ኢትዮጵያውያን "የመንግስት ኢኮኖሚያዊ አፈጻጸም እጅግ ደካማ ነው" ም ብለዋል ‼️

👉🏼 መንግስት በበኩሉ "ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እያስመዘገብሁ ነው" ይላል

አፍሮ ባሮ ሜትር እ.ኤ.አ. ከግንቦት 25 - ሰኔ 22 ቀን 2023 ዓ.ም የመንግስት ኢኮኖሚያዊ አስተዳደር [ አፈጻጸም ] በተመለከተ ኢትዮጵያውያንን አነጋግሮ ያጠናቀረውን ዳሰሳዊ ጥናት ከ12 ቀናት በፊት ይፋ አድርጓል።

በዚህም ድርጅቱ ካነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን መካከል አብዛኞቹ መንግስት ኢኮኖሚ ላይ ያለው አፈጻጸም እጅግ የከፋ [ ደካማ ] መሆኑን ተናግረዋል።

ከ56 በመቶ በላይ ኢትዮጵያውያን ሀገራቸው በትክክለኛው ሀዲድ እየተጓዘች ነው ብለው አያምኑም። የስህተት ጎዳና ጉዟዋን ተያይዛዋለች ባይ ናቸው መባሉን ዳጉ ጆርናል ከአሻም ዘገባ ተመልክቷል።

ምንም እንኳን መንግስታዊ አሐዞች እና የባለስልጣናቱ መግለጫዎች አወንታዊ ኢኮኖሚያዊ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ቢገልጹም አፍሮ ባሮ ሜትር ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን ግን የሰጡት አስተያየት ከዚህ የተቃረነ ነው።

የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም[ UNDP ] የፈርጀ ብዙ የድህነት ጠቋሚ [Multi dimensional poverty Index ] መሠረት ድህነት ከተንሰራፋባቸው ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ከፊተኞቹ ተርታ መሰለፏን ከአንድ ሳምንት በፊት ባወጣው ሪፖርት አመልክቷል።

Via _አሻም

https://t.me/satenawmedia1

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

26 Oct, 11:41


#ደመወዝ‼️
ደመመዝ እንዲከፈላቸው ፊርማ ያሰባሰቡ የ #ዎላይታ ዞን መምህራን ለእስር ተዳረጉ‼️
በ #ደቡብ_ኢትዮጵያ ክልል ዎላይታ ዞን ደመወዝ እንዲከፈላቸው ፊርማ በማሰባሰብ ላይ የነበሩ መምህራን ለእስር መዳረጋቸውን የታሳሪ ቤተሰቦች ገለፁ።
እስሩ የተፈጸመው መምህራኑ ከደመወዝ ጥያቄ ጋር በተያያዘ ፊርማ በማሰባሰብ ለኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አቤቱታቸውን ለማስገባት በሚንቀሳቀሱበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል።

ፖሊስ መምህራኑ "አመፅ ለመቀስቀስ ተንቀሳቅሰዋል" እንዲሁም "የዞኑን ገጽታ አጥፍተዋል" በሚል ማሰሩን የታሳሪ ቤተሰቦች ገልፀዋል።

"ፖሊሶች ወደ ቤት ሲመጡ ምንም አይነት የፍርድ ቤት መያዣ ወረቀት አላሳዩም" ያሉት የመምህራኑ ቤተሰቦች አክለውም መምህራኑ ደሞዝ ይሰጠን ብለው የዳቦ ጥያቄ በማንሳታቸው ብቻ ታሰረውብናል ሲሉ ገልጸዋል።

እንዲሁም አንድ የዳሞት ወይዴ ወረዳ መምህር በበኩላቸው የፊርማ ማሰባሰብ ስራውን ሲያስተባብሩ ከነበሩት መካከል ሶስት በቅርብ የሚያውቋቸው መምህራን ለእስር መዳረጋቸውን ገልጸው፤ ከመታሰራቸው በፊት "እረፉ" የሚል ማስጠንቀቂያ ከወረዳው ባለሥልጣናት ተሰጥቷቸው እንደነበረ ገልጸዋል።

የዎላይታ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ግንባር ዎህዴግ ሊቀመንበር የሆኑት አቶ ጎበዜ ጎኣ በበኩላቸው መምህራኑ ያነሱት የደመወዝ ጥያቄ ተገቢ መሆኑን ጠቅሰው፤ "ደመወዝ የጠየቀን አመፅ ቀስቀሰሃል ብሎ ማሰር ከሥነምግባር ውጭ የሆነ ድርጊት ነው" ብለዋል።
#ዶቸቬለ
👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

26 Oct, 11:03


የብልፅግና አመራሮች 27ቱ ጥያቄዎች!

ገዢው የብልጽግና ፓርቲ፣ “የህልም ጉልበት ለእመርታዊ እድገት” በሚል ስያሜ፣ ለፓርቲው አመራሮች ሦስተኛውን ዙር ሥልጠና በመላ አገሪቱ እየሰጠ ይገኛል።

በአዲስ አበባ እየተሰጠ ስላለው የፓርቲው አመራሮች ሥልጠና ዋዜማ እንደሰማችው ከሆነም፣ ከሳምንት በፊት ለ10 ቀናት ስልጠናውን የወሰዱ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች በርከት ያሉ ጥያቄዎችን በግላቸው አቅም ብቻ ሰርተው እንዲመልሱ ተደርጓል።

ከባለፈው ሰኞ ዕለት ጀምሮም፣ ለ11 ቀናት የሚቆየውን እና ሦስተኛውን ዙር ስልጠና እየተካፈሉ ያሉ የፓርቲው አመራሮችም፣ እነዚሁኑ ሃያ ሰባት የሚሆኑ ጥያቄዎች፣ እርስ በእርስ ሳይመካከሩ መመለስ ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።

ዋዜማ ሬዲዬ እንደዘገበው “የዳቦ ጥያቄ እያለ የኮሪደር ልማት ለምን መስራት አስፈለገ?” ለሚል ጥያቄ ጭምር  ምላሽ እንዲሰጡ ተጠይቀዋል።
ጥያቄዎቹ:-
1. አንድ ሰው ዘርፈ ብዙ ሀገራዊ ችግሮች እያሉ ወይም የዳቦ ጥያቄ ሳይመለስ ለምን የኮሪደር ልማት ትሰራላቹ ቢል ምላሻችን ምንድነው?የኮሪደር ልማት መፍጠር ለምንፈልገው ኢኮኖሚ እና ማሳካት ለምንፈልገው ማህበራዊ ግብ ያለው ዋጋ ምንድነው?

2. የብልፅግና ማዕከልነት ምንድነው? ከፖለቲካ፣ ከኢኮኖሚ እና ከውጭ ጉዳይ አንጻር የሀሳብ መነሻዎችን እና ተግባራዊ ምሳሌዎችን በመጥቀስ አስረዱ? ከትርክት አንጻር በመዳሰስ አስረዱ?

3. አገልጋይነት ስነ-ምግባራዊ አመራር የሚያደርገው ምንድነው?አገልጋይነት ከሌሎች አመራር ዘዴዎች የተለየ የሚያደርገው ምንድነው?አገልጋይ መሪነት ለብልፅግና ተመራጭ የሚሆነው ለምንድነው?

4. የመደመር መሰረታዊ እሳቤ ከብሔራዊነት ትርክት እና ከህልማችን ጋር ያለው ትስስር ምንድነው?የብሔራዊነት ትርክት እና የሀገራዊ ህልም ትስስር ምንድነው?

5. ህልውና መር አካሄድን ከሀገራችን ታሪክ ጋር በማያያዝ አስረዱ? ያመጣው ውጤት እና የፈጠረው ውድቀት ምንድነው?

6. ብልፅግና የእይታ እና የምናብ ለውጥ ነው፡፡ ይህንን የእይታ ለውጥ ከታሪክ ምልከታ እና እጣፈንታችን ከመወሰን አንጻር አስረዱ?

7. የተለያዩ የተሰሩ ስራዎችና ኢንሼቲቮች መነሻ ህልም እና የሚፈጥሩት አለም እና አቅም ምንድናቸው?

8. ሳይንስ ሙዚየም፣ አብርሆት፣ ገበታ ፕሮጀክቶች ከፍ ያለ ምናብ እና አርቆ እይታ ውጤቶች ናቸው ሲባል ምን ማለት ነው? ህልማችንን ልዕልና መር የሚያደርገው ምንድነው? የህልማችን መዳረሻ እና ተግባራዊ ምሳሌዎችን በማገናኘት አስረዱ?

9. የፖለቲካ ገበያ የጋራ ህልማችን እንቅፍት ነው ሲባል ምን ለማለት ነው?

10. በነባራዊና አለም አቀፋዊ ትንታኔያችን ውስጥ ብዝሀ ቀውስ፣ የመረብ ዘመን እና ድህረ-እውነት የሚሉ ጉዳዮችን ደጋግመን እንገልጻለን፡፡ እነዚህ ጉዳዮች በማያያዝ እና በማሰናሰል ነባራዊ አለም አቀፍ ሁኔታ ምልከታችንን አስረዱ? እነዚህ እውነታዎች ከሀገራችን ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚ እና ዲፕሎማሲ አንጻር እየፈጠሩ ያሉትን እና የሚኖረውን አወንታዊ እና አሉታዊ ተጽዕኖ አስረዱ?

11. የስነ-ምግባር አስተውሎት/ኢንተለጀንስ ለአመራሩ ቁልፍ የሚያደርገው ምንድነው? ብልፅግናን ለማረጋገጥ እና ለመደመር ስነ-ምግባር አስፈላጊ ነው ቢባል ምን ለማለት ነው?

12. የለውጥ ዋና ዋና ስኬት ከሆኑት ውስጥ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና በውጭ ግንኙነት ውጤቶች አንዳንድ በመዘርዘር ከእነዚህ ውጤቶች ጀርባ ያለውን የሀሳብ መነሻ እና የአካሄድና የመንገድ ልዩነት አስረዱ?

13. የህግ ማስከበር ተቋማት ሪፎርም በተቋማት ውስጥ እና በሀገር ግንባታ ውስጥ የፈጠረው ለውጥ እና ያመጣውና የሚያመጣው ተጽዕኖ ምንድነው?

14. ተቋማት ግንባታ የለውጡ መሰረታዊና ቁልፍ ጉዳይ የሆነው ለምንድነው? አመራሩ በተቋማት ግንባታ ውስጥ የሚጫወተው ሚና ምንድነው?

15. የፖለቲካና የኢኮኖሚ ሪፎርም ስራዎቻችን ከህልማችን መዳረሻ እና ስኬት ጋር በማያያዝ አስረዱ?

16. ህልውና መር እይታ ከችግር የማያሻግር የተባለበት ምክንያት ምንድነው?

17. የሀገራዊ ህልማችን ቁልፍ መዳረሻዎች ምንድናቸው? በዝርዝር አስረዱ?ህልምን ለማሳካት እንቅፋቶች ምንድናቸው? ህልምን ለማሳካት ከአመራሩ ምን ይጠበቃል?

18. የፖለቲካ ሪፎርም ማድረግ ለምን አስፈለገ? የፖለቲካ ሪፎርም ገፊ ምክንያቶች፡-የፖለቲካ ሪፎርም ማድረግ ያስፈለገበት ምክንያት፡-የሪፎርሙ መሰረቶች ምንድናቸው? ውጤታማነቱስ እንዴት ይመዘናል? የፖለቲካ ሪፎርም ውጤታማነት መመዘኛዎች፡-የመሃል ፖለቲካን ባህሪያትና ፋይዳ ተረድቶ የመምራት አስፈላጊነትን አስረዱ? የጠንካራ ፓርቲ ግባችንን ማሳካት ለህልማችን እውን መሆን ያለውን ፋይዳ አስረዱ?የጠንካራ ፓርቲ ግባችንን ማሳካት ለህልማችን እውን መሆን ያለውን ፋይዳ፡-ፓርቲያችንን ለማጠናከር ከአመራሩ ምን ይጠበቃል?

19. የኢኮኖሚ ሪፎርም ማድረግ ለምን አስፈለገ? የሪፎርሙ አንጓዎች ምንድናቸው? ምን አይነት ውጤትስ ያመጣል?

20. አብዮታዊ ዲሞክራሲ እና መደመር ቁልፍ ልዩነቶችን አስረዱ? በኢኮኖሚ፣ በፖለቲካ እና በውጪ ግንኙነት የምንከተላቸው መንገዶች ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ ጋር ያለውን ልዩነት በዝርዝር አስረዱ?

21. የሰላም እጦት ቁልፍ ምክንያቶች ምንድናቸው?የብልጽግና የሰላም ግንባታ ግብ ምንድነው? ሰላምን ለማምጣት የምንከተለው አካሄድ ከነባሩና ከተለመደው አካሄድ ጋር ያለው ልዩነት ምንድነው? ሰላምን ለማረጋገጥ ያደረግናቸው ጥረቶች እና የመጡት ውጤቶች ምንድናቸው? የገጠሙን ተግዳሮቶችስ?

22. ከለውጡ በኃላ ብዙ ኢንሼቲቮች ተጀምረው ውጤት አምጥተዋል፡፡ ከእነዚህ ኢንሼቲቮች ጀርባ ያለው ሀሳብ፣ የተሰሩበት መንገድ፣ የሚያመጡት ውጤት ምን ለመድረስ  እና ለመፍጠር በማመን ነው? ከሀሳቦቻችን ጋር በማስተሳሰር አስረዱ? እየፈጠሩት ያለው የአመለካከት እና የባህል ለውጥ አስረዱ?

23. የምግብ ሉዓላዊነት የብልጽግና ቁልፍ አጀንዳ ሆነ? የምግብ ሉዓላዊነት ግቦቻችን   ምንድናቸው? የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ እየተሰሩ ያሉ ዋና ዋና ስራዎች ምንድናቸው? ያመጡት ውጤትስ?

24. የህዳሴው ግድብ መጠናቀቅ ያለውን ቁልፍ ሀገራዊ ፋይዳ አብራሩ? ከኢኮኖሚ፣ ከፖለቲካ፣ ከተቋማት መፈጸም ብቃት እና ከዲፕሎማሲ አንጻር?

25. የለውጡ የውጭ ግንኙነት ዋነኛ የአመለካከት እና የተግባር ልዩነት ምንድነው? ዘላቂ ወዳጅነት የመሰረትንባቸው ሀገራት እነማን ናቸው?

26. ለስኬት እያበቁን ያሉ ቁልፍ የአመራርነት ሚናዎች ምንድናቸው? በሀገራችን ቁልፍ የአመራር ክፍተቶች እና ውድቀቶች ምንድናቸው? በተለይም ለችግር እየዳረጉን ያሉ ቁልፍ የአመራር ክፍተቶች ምንድናቸው?

27.  በአመራር ክፍተት ምክንያት የተፈጠሩ ወይም የተባባሱ ቁልፍ ሀገራዊ ችግሮች ምንድናቸው? እንደ ብልጽግና  አመራር ካለፈው መማር እና ማዳበር ያለብን ቁልፍ የአመራርነት ክህሎቶች ምንድናቸው? አንድ አመራር የብልጽግና አመራር የሚሆነው ምን ሲሆን ነው?ፓርቲያችን የአመራርን ክፍተት ለማረም እየተከተለው ያለው ስትራቴጂ ምንድነው? ምን ይጎድለዋል? ምን ይታረም?
ከዚህ አመራር የቀሰሙትን እውቀት እና ያገኙትን ውጤት ከሚመሩት ተቋም፣ ከሚመሩት ክልል፣ ዞን ጋር በማስተሳሰር በዝርዝር አስረዱ? ከስልጠናው ተነስተው ቀጣይ ግለሰባዊ እቅድ እና ተቋማዊ እና አስተዳደራዊ እቅድ በዝርዝር ያስቀምጡ?

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

26 Oct, 02:55


#USA ‼️

ትራምፕ ቢያሸንፍ ለአለም ምን ለዉጥ ያመጣል...!?🙌

የትራምፕ መምጣት የሚያሰጋቸው እነማን ናቸው...!? ለምን...!?

📌የአሜሪካ ምርጫ 11 ቀናት ብቻ ቀረው እየተባለ ነው። ቀድሞ መምረጥ የፈለገ መምረጥ ከጀመረ ሰነባብቷል። መቸም የአሜሪካ ምርጫ አሜሪካኖችን ብቻ ሳይሆን ቅሉንም ጨርቁንም ነው የሚያነጋግረው። በተለይ አውሮፓውያን ከሃገራቸው ምርጫ ይልቅ የአሜሪካ ምርጫ ነው የሚያስጨንቃቸው። ወሬያቸው በሙሉ "ትራምፕ እየመጣ ነው፣ ጉድ ሊፈላ ነው!" የሚል ነው። የትራምፕን መምጣት በጭንቀት ተወጠረው እየተጠባበቁ እንደሆነ ለመደበቅ እንኳን አይሞክሩም። ከአሜሪካ ሊብራሎች ባልተናነሰ ምናልባትም በከፋ ደረጃ የትራምፕን መምጣት የማይፈልጉት አውሮፓውያን ናቸው ቢባል ብዙ ማጋነን አይሆንም። ከአራት አመታት በፊት ስልጣን ላይ በነበረበት ጊዜ ያደረገውን ያስታውሳሉ። የአሜሪካ የጭን ውሾች የሆኑት አውሮፓውያን ትራምፕ  "አላስነካችሁም!" ብሉ መከራቸውን አብልቷቸዋል። እንደ ሰፈር ጎረምሳ ወይንም የሽፍታ አለቃ "ገንዘብ ካልከፈላችሁኝ ለደህንነታችሁ ዋስትና አልሰጥም!" ብሎ አስደንግጧቸዋል። ከአለም አቀፉ የፓሪስ የአካባቢ ብክለት ስምምነት አሜሪካንን ከመሳብ አልፎ ከሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን ወይንም (NATO) ስምምነትም እውጣለሁ እያለ ሲያሸብራቸው ቆይቷል። አሁንም ቢሆን "ስልጣን ላይ ልውጣ እንጂ ሁልሽንም ልክ አስገባለሁ!" እያለ ነው። ትራምፕ ከመጣ ዩክሬይን ከሩስያ ጋር ከመስማማት ውጪ አማራጭ አይኖራትም። አውሮፓውያን እንደሆኑ አሜሪካንን ተከትለው ካልሆነ በስተቀር ለብቻቸው ዩክሬይንን ለማስታጠቅ እጃቸውን እንደማያነሱ የታወቀ ነው። በመሰረቱ አውሮፓውያንም ሆኑ የባይደን አሜሪካ ዩክሬይንን እያስታጠቁ ያሉት ዩክሬይን ሩስያን ታሸንፋለች በሚል ሳይሆን በዩክሬናውያን የህይወት መስዋእትነት ሩስያን እናዳክማለን በሚል ስሌት ነው። ለፖለቲካ ቁማር ጨዋታ እንግዳ የሆነው ትራምፕ ይሄ አይነቱ ስሌት አይገባውም። ስለዚህ በግዢ እንጂ በነፃ የሚሰጥ ነገር በትራምፕ አለም ቦታ የለውም።

ከአውሮፓውያን ውጪ የትራምፕ መምጣት የሚያስጨንቀው ብዙ አይደለም። "ትራምፕ የመጣ እንደሆነ እስራኤል ፈቶ ይለቅብናል" የሚሉ አንዳንድ ድምፆች ከአንዳንድ ሙስሊሞች ሲነገር ይደመጣል፣ ነገር ግን ብዙዎች በትራምፕና ራሱን በይፋ "ጽዮናዊ ነኝ!" በሚል በኩራት በሚያውጀው ባይደን መካከል ምንም ልዩነት እንደሌለ ነው የሚያምኑት። ትራምፕ ባይደን ያላደረገውን ምን ማድረግ ይችላል ብለን ብንጠይቅ አጥጋቢ መልስ የምናገኝ አይመስልም። ባይደን ለእስራኤል መሳሪያ ከማስታጠቅ፣ የዲፕሎማሲ ድጋፍ ከመስጠት፣ ከጥቃት ከመከላከል አልፎ የአሜሪካ ወታደሮችን እስከመላክ የዘለቀ ድጋፍ አድርጓል። ከዚህ በላይ ምን የሚደረግ ነገር አለ? እንዲያውም የትራምፕ መምጣት አውሮፓውያንን ገለል ስለሚያደርግና አውሮፓውያኑ ራሳቸውን ችለው አቋም እንዲይዙ ሊያስገድዳቸው ስለሚችል በጎ ጎን ሊኖረው ይችላል የሚሉ አሉ።

በተረፈ ግን አረቦችን ጨምሮ ቻይናም ትሁን ሩስያ የትራምፕን መምጣት በጉጉት የሚጠብቁት ነው የሚመስሉት። ትራምፕ የተመረጠ እንደሆነ አሜሪካ ትልቅ የውስጥ ቀውስ ውስጥ እንደምትገባ መገመት ይቻላል። ትራምፕ የፖለቲካን ጨዋታና ባህል የማያውቅ ብቻ ሳይሆን ለማወቅም የማይፈልግ፣ በራሱ ሃሳብና ፍላጎት ብቻ የሚመራ፣ ለህግ የበላይነት ቅንጣት ታክል ክብር የሌለው፣ ቢቻለው አምባገነን መሪ ለመሆን የሚመኝ ሰው በመሆኑ ለአሜሪካ የልብ ህመም እንደሚሆን ይታሰባል። የአሜሪካ ልብ ህመም ደግሞ ለሌሎች በአሜሪካ ሶፍትና ሃርድ ፓወር መከራቸውን እያዩ ላሉ ሀገራት የልብ ፈውስ እንኳን ባይሆን በእፎይታ የመተፈሻ ጊዜ ሊሰጣቸው እንደሚችል ይገመታል። በተለይ እንደ ብሬክስ ያሉ በመቋቋም ላይ ያሉ አለም አቀፋዊ ተቋማት ከትራምፕ ሥልጣን ላይ መውጣት ጋር ተያይዞ ሊፈጠር የሚችለውን የአሜሪካ ቀውስ በመጠቀም አቅማቸውን ሊያጎለብቱ የሚችሉበት መልካም አጋጣሚ ሊፈጠርላቸው ይችላል። ለማንኛውም በሐያት ቆይተን የሚሆነውን ለማየት ያብቃን!😍 አሜን!🙏

🗣 የናንተንም ሃሳብ አካፍሉን!‼️
https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

26 Oct, 02:52


"በመንግሥት በኩል አስክሬናቸውን የመፈለግ ሥራ ቆሟል"  -የክልሉ ኮምዩኒኬሽን

በጋምቤላ ክልል መስከረም 15/2017 ዓም  ከጋምቤላ ከተማ ወደ ኑዌር ዞን በመጓዝ ላይ የነበረ አምቡላንስ በጂካዎ ወረዳ የባሮ ወንዝ ጊዜያዊ ድልድይን ጥሶ በወንዝ ውስጥ በመግባቱ 7 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የክልሉ ኮምዩኒኬሽን ገልጾ ነበር።

አደጋው ካጋጠመ በኋላ በተደረገ ፍለጋ የአንድ ሰው አስክሬን ማግኘት ቢቻልም ሲጓጓዙበት የነበረውን አምቡላንስ ጨምሮ ቀሪ ስድስት አስክሬኖች እስካሁን አልተገኙም።

በዛሬው ዕለት አንድ ወር የሆነው ይህ አደጋ አስክሬናቸውን የመፈለጉ ሥራ በመንግስት በኩል መቆሙን የክልሉ የህዝብ ግንኙነት ባለሞያ የሆኑት አቶ ኦጁሉ ጊሎ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ከሟቾች መካከል በክልሉ ኑዌር ዞን የሚገኘው ኒን ያንግ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሠራተኞች የሆኑት 7 ሰዎች ነበሩበት።

በአደጋው ለተጎዱ ቤተሰቦች የዓይነት ድጋፍ መደረጉን ያነሱት ባለሞያው አስክሬናቸውን የመፈለግ ሥራው ግን የባሮ ሃይቅ እስካሁን ባለመጉደሉ እና በከፍተኛ ፍጥነት የሚምዘገዘግ በመሆኑ የአምቡላንሱንም ሆነ የአስክሬናቸውን አቅጣጫ ይለውጣል "አይገኝም" ነው ያለት።

የባሮ ወንዝ የሚቀንስበት ወቅት ከህዳር በኋላ ነው ያሉት አቶ ኦጁሉ አሁን ባለበት ሁኔታ ግን ምንም መቀነሱን የሚያሳይ ምልክት የለም ሲሉ ነው የገለጹት።
Via Tikvah

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

25 Oct, 18:38


ታላቁ የኢትዮጵያ የእግርኳስ ተጫዋችና አሰልጣኝ አስራት ሀይሌ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ‼️

በኢትዮጵያ እግርኳስ ስማቸው በወርቅ ቀለም በደማቅ ታሪካቸው ከተፃፈላቸው የእግርኳስ ሰዎች መካከል አንዱ የነበረው አሰልጣኝ አስራት ኃይሌ (ጎራዴው) በመጨረሻም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ከ60 ዓመታት በላይ በዘለቀ የተጫዋችነት እና የአሰልጣኝነት ህይወቱ ሀገሩን ሳይሰስት ባገለገለው አስራት ኃይሌ ህልፈት ዳጉ ጆርናል የተሰማዉን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው የእግር ኳስ ቤተሰብ መፅናናትን እንመኛለን።

Via_dagu

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

25 Oct, 17:02


#ፓስፖርት ለማውጣት "የአምስት ሺሕ ብር ሲስተም የለም" እየተባልን ነው ሲሉ ተገልጋዮች ቅሬታ አቀረቡ

የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት 20 ሺሕ እና 25 ሺሕ ብር ከሚያስከፍሉት የአስቸኳይ አገልግሎቶች በስተቀር በመደበኛ ከፍያ እያስተናገደን አይደለም ሲሉ ተጋልጋዮች ቅሬታቸውን አቅርበዋል፡፡

ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ "5 ሺሕ ብር ከፍለን በመደበኛው ጊዜ ፓስፖርታችንን መውሰድ አልቻልንም" ያሉ ሲሆን፤ "ለዚህም የሚሰጠን ምክንያት ‹‹ሲስተሙ አይሰራም›› የሚል ነው" ብለዋል፡፡

አክለውም "የፓስፖርት አገልግሎት ክፍያውን መምረጥ ያለበት ተጠቃሚው ነው፡፡" ያሉ ሲሆን፤ "በ2 ቀን እንዲደርስላችሁ 25 ሺሕ ብር በ10 ቀን እንዲደርስላችሁ ደግሞ 20 ሺሕ ብር ክፈሉ መባላችን ትክክል አይደለም፡፡ በመረጥነው ክፍያ ልንስተናገድ ይገባል" ሲሉ ለአሐዱ ተናግረዋል፡፡

ኢትዮጵያ አዲስ የማክሮ ኢኮኖሚይ ማሻሻ ማድረጓን ተከትሎ፤ የክፍያ መሻሻሎች ካደረጉ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች መካከል አንዱ፤ የኢትዮጵያ ኤምግሬሽን የዜግነት አገልግሎት መሆኑ ይታወቃል።

የኢምግሬሽን የዜግነት አገልግሎት ለዜጎች  ፓስፖርት ለመስጠት ሲል የክፍያ እና የጊዜ ቀነ ገደብም አስቀምጧል፡፡

ዜጎች በሁለት ወራት ውስጥ ፓስፖርት ለማግኘት ዝቅተኛው ክፍያ አምስት ሺሕ ብር መሆኑን አገልግሎቱ  በወቅቱ ያሳወቀ ቢሆንም፤ ተገልጋዮች "አምስት ሺሕ ብር ከፍሎ  ፓስፖርት የማግኘት ሲስተም ለጊዜው የለም እየተባለን እየተመለስን ነው" ሲሉ ተናግረዋል።

ሌላኛው ሥማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ተገልጋይ በበኩላቸው፤ "የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት ወደ ኢምግሬሽን የዜግነት አገልግሎት የሄድን ቢሆንም፤ ከመጉላለት በዘለለ በፓስፖርት ወረፋ ወቅት ያለው ወከባ እና ግርግር ለደህንነታችን አስግቶናል" ብለዋል፡፡

አሐዱ "ለአስቸኳይ ከፍተኛ ከፋዮች የሚሰራው ሲስተም ለዝቅተኛ ከፋዮች የማይሰራበት ምክንያት ግልጽ አይደለም" የሚለውን የተገልጋዮች ቅሬታ በመያዝ ከኢትዮጵያ የኢምግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ምላሽ ለማግኘት በተደጋጋሚ ያደረገው ሙከራ፤ የአገልግሎቱ የሥራ ሃላፊዎች ስልክ ባለማንሳታቸው እንዲሁም አንስተው "ጉዳዩ አይመለከተንም" በማለታቸው ምክንያት ምላሹን ማካተት አልቻለም፡፡

(አሀዱ ሬዲዮ)

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

25 Oct, 16:59


ባለሃብቱ አቶ መቅደስ አክሊሉ ፍርድ ቤት ቀረቡ ‼️

ዓርብ ጥቅምት 15 ቀን 2017 ላለፉት ሶስት ቀናት በጸጥታ ሃይሎች ተይዘው የነበሩበት ያልታወቀው ባለሀብቱ አቶ መቅደስ አክሊሉ ዛሬ ፍርድ ቤት መቅረባቸው ተገልጧል፡፡

አቶ መቅደስ የአቢሲኒያ ባንክ ዋና ባለ ድርሻ ሲሆኑ ለምን በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የታወቀ ነገር አለመኖሩ የተነገረ ሲሆን ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበው የ13 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንደተሰጠባቸውም ታውቋል::

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

25 Oct, 16:45


#ትምህርት ሚንስቴር


ከዚህ በፊት ለሪሚዲያል ተማሪዎች በተቋማት የሚሰጠው ውጤት 30% ሲሆን 70% ደግሞ የሚሰጠው ከት/ት ሚኒስቴር ነበር።

አሁን ግን ይህ አሠራር ተሻሽሎ 100% ከማዕከል(በትምህርት ሚኒስቴር በሚሰጡ ምዘናዎች) በኩል እንዲሰጥ ተወስኗል።

ተማሪዎች በሚማሩት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጠው 30% የውጤት ምዘና  አሰጣጡ ወጥነት ስለሚጎድለው ይሄን ማሻሻያ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አክሎ ገልጿል።
via_atc

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V

ሳተናው ሚዲያ / Satenaw Media

25 Oct, 16:44


🇧🇴🌐 ቦሊቪያ ብሪክስን እንደ አጋር ሀገር ተቀላቅላለች ሲሉ ፕሬዝዳንት ሉዊስ አርሴ ተናገሩ ‼️

"የእኛዋ ፕሉሪኔሽናል ሀገር ቦሊቪያ ብሪክስን በመላቀል ትልቅ እርምጃ ወስዳላች ፣ የህብረቱ ሀገራት ቦሊቪያ እንደ አጋር ሀገር መቀበላቸውን ነግረውናል" ሲሉ አርሴ በቴሌግራም ላይ ጽፏል።

የቦሊቪያው ፕሬዝዳንት አክለውም ይህ እርምጃ የቦሊቪያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ከፍተኛ ስኬት ያስመዘገበ ሲሆን በውጤቱም ሁለገብ እንድንሆን ያስችለናል ብለዋል።

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን  የብሪክስ አባል ሀገራት በሩሲያ ካዛን በተካሄደው የመሪዎች ጉባኤ ላይ የአጋር ሀገራት ዝርዝር ላይ መስማማታቸውን ቀደም ሲል ገልፀዋል።

https://youtu.be/KIm76uhWoOw?si=iren3RQ3tiEVll6V