ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan) @mahibere_kidusan Channel on Telegram

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

@mahibere_kidusan


The channel of mahibere kidusan

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan) (Amharic)

ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan) የተጨመረው በረረ ታሪክ የማይረሳህ አልባሳቢ፣ መብትና ቅዱሳን ምክር ግንባታ ከሚያደርጉ በፊት አንዳንዴ የዚህ አርብ ማኅበረ ቅዱሳን ብቻ ነው። ይህ ባህላዊ በመሆኑ የሆላችሁት ትምህርት ከመካከላችሁ፣ ደምህን ለማሳዛና መረገም ለማነጋገር በቀደም ጊዜ እና ማንኛውም እናት እና አባት እና ልጅ ካልሆነ ተምረን ህግደፍት ከእናንተ እጅ ለመባለል የሚገኘው ባማኖች እና ብሄራዊ ገዢዎች ተጨንጫለች። ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan) ተስፋፊያና የሊቀ ረከት፣ መጣጥመንና ህክምና መኖ ማሃዳ ላይ እንዲሆን ነው። ማኅበረ ቅዱሳን (Mahibere Kidusan) እና የቸሪልም መረጃዎች ለመረጃንድ በለጠ መረጃ፦ ሌላ ለጸጋም ምርታማነትም ለሥራ እሾክና ሉቃል ተባባሉ።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

15 Feb, 07:50


፲፫ተኛው የግቢ ጉባኤያት ሴሚናር ከየካቲት 21 እስከ የካቲት 23 እንደሚካሄድ ተገለጸ።

የካቲት ፰/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ አማካኝነት በየሁለት ዓመቱ የሚዘጋጀው ፲፫ተኛው የግቢ ጉባኤያት ሴሚናር ከየካቲት 21 እስከ የካቲት 23/6/2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ በማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማስተባበሪያ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበበ በዳዳ ገልጸዋል።

ሥራ አስፈጻሚው እንደገለጹት የመርሐ ግብሩ ዓላማ በከፍተኛ የት/ት ተቋማት የሚማሩ  ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች በቤተ ክርስቲያን አሁናዊ ሁኔታና በማኅበረ ቅዱሳን በአጠቃላይ የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዙሪያ እየተከናወኑ ስላሉ ተግባራት ግንዛቤ የማስጨበጥና የበለጠ ለማገልገል እንዲተጉ ለማድረግ የተዘጋጀ እንደሆነ  አስታውቀዋል።

አክለውም ከ43 ማእከላት የተወጣጡ 450 የግቢ ጉባኤ አገልግሎት ዋና ክፍል አባላትና ተሳታፊዎች እንዲገኙ እንደ ዕቅድ የተያዘ ቢሆንም አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታና በበጀት እጥረት ምክንያት ከ300 በላይ ተሳታፊዎች እንደሚገኙ ይጠበቃል ብለዋል።

ሴሚናሩ በሁለት ዓመት አንድ ጊዜ የሚከናወን ሲሆን ማኅበሩ በግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ላይ እያከናወነ ያለውን ተግባር ለመገምገም እና  ለወደፊት የተሻሉ አቅጣጫዎች ለማስቀመጥ እንደሚያግዝ ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ወጣቶች መንፈሳዊ አገልግሎትን እና ቤተ ክርስቲያንን እንዲያውቁ በግቢ ጉባኤያት በኩል እያስተማረ እንደሚገኝ የገለጹት አቶ አበበ አያይዘውም የተማሪ ወላጆች ልጆቻቸውን ለከፍተኛ ት/ት ተቋማት ሲልኩ ወደ ግቢ ጉባኤያት መሄድና መማር እንዲችሉ በማድረግ በሁለቱም በኩል እንዲጠነክሩ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው መልእክት አስተላልፈዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

15 Feb, 06:32


https://youtu.be/PZqzTBkxDQA?feature=shared

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

13 Feb, 08:23


“ሃሎ መምህር” የተሰኘ ለሃይማኖታዊ ጥያቄዎች በስልክ ምላሽ የሚሰጥ አገልግሎት መጀመሩ ተገለጸ።

የካቲት ፮/፳፻፲፯ ዓ.ም

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት “ሃሎ መምህር” የተሰኘ ለሃይማኖታዊ ጥያቄዎች በስልክ ምላሽ የሚሰጥ አገልግሎት መጀመሩን አስታውቋል።

የስብከተ ወንጌልና ዕቅበተ እምነት ዋና ክፍል ምክትል ኃላፊ ዲያቆን ዐብይ ጌታሁን እንደገለጹት አገልግሎቱ በዋናነት የስብከተ ወንጌልን ተልዕኮ ለማዳረስ በተለይ በቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ምዕመናንን በእምነታቸው እንዲጸኑ ለማድረግና ከአዳዲሰ አማንያን የሚመጡ ጥያቄዎችን ለመመለስ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።

ከተጀመረ 5 ቀን የሆነው ይህ አገልግሎት ከ 30 እስከ 40 ለሚሆኑ ምዕመናን ለጠየቋቸው ጥያቄዎች ምላሽ መሰጠቱን በመግለጽ ሰዓቱን ያልጠበቁ የስልክ ጥሪዎችን ለማስተናገድ ፈተና እንደሆነባቸው አክለው ገልጸዋል።

በዚህም ዘወትር ከሰኞ እስከ ዓርብ ከጠዋቱ 4፡00 - 10፡00 ሰዓት አገልግሎቱ የሚሰጥ ሲሆን ሰኞ፣ ረቡዕና ዓርብ በኦሮምኛና በአማርኛ እንዲሁም ማክሰኞና ዓርብ በአማርኛ ቋንቋ ብቻ እንደሚሰጥ ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ም/ኃላፊው የምዕመናን ተሳትፎ ጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው “በተለያየ ምክንያት መማር ያልቻሉ፣ ጥያቄ የፈጠረባቸውና በአካል መገኘት ለማይችሉ ምዕመናን በያሉበት ስልክ በመደወል ጥያቄዎችን በመጠየቅ ምላሽ ማግኘት ቢችሉ ከሃይማኖት እንዳይወጡና ከቤተ ክርስቲያን እንዳይለዩ ይረዳቸዋል” በማለት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

12 Feb, 07:21


ዕቅበተ እምነትና ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ  ጉባኤ መካሄዱን በማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ታቦር ማእከል አስታወቀ ።

የካቲት ፭/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ታቦር ማእከል ዕቅበተ እምነትና ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ላይ ያተኮረ ሕዝባዊ ጉባኤ ከየካቲት 01- 02/02/2017 ዓ.ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት በደብረ ታቦር ደብረ ልዑላን መድኃኔዓለም ቤ/ክ አከናውኗል።

በመርሐ ግብሩ መምህረ መምህራን የኔታ በጽሐ ዓለሙ በደ/ታቦር ደ/ልዑላን መድኃኔዓለም ቤ/ክ የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር መምህር፣ መ/ር ልሳነወርቅ አእምሮ የጉባኤ ቤቱ የሐዲሳት መምህር እና መ/ር ተመስገን ዘለዓለም በፍኖተ ሰላም ምሥራቀ ፀሐይ አቡነ ቶማስ መታሰቢያ የመጻሕፍት ጉባኤ ቤት የሐዲሳት መምህር ተገኝተዋል።

መምህራኑም ዕቅበተ እምነትና ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ላይ ትኩረት ያደረገ ማብራሪያ በትምህርት እና በምክረ አበው መልኩ ሰጥተዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

11 Feb, 08:11


በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የገጽ ለገጽ ስብስባ ማካሄዱ ተገለጸ።

የካቲት ፬/፳፻፲፯ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን በአውሮፓ ማእከል የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት የዘንድሮውን ዓመት የገጽ ለገጽ ስብሰባ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ከተማ ደብረ ምሕረት ቅዱስ አማኑኤል ቤተ ክርስቲያን ከጥር 30 እስከ የካቲት  2 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂደዋል።

በስብሰባው የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ዘሚካኤል ዴሬሳ፣ አገልጋይ ካህን ቀሲስ ኃይለ ጊዮርጊስና የዴንማርክ ግንኙነት ጣቢያ አባላት ተገኝተዋል።

በዚህም የማእከሉ የ6 ወራት የአገልግሎት አፈጻጸም፣ የንዑሳን ማእከላትና የግንኙነት ጣቢያዎች አሁናዊ ሁኔታ ምን እንደሚመስል በመምከር ለቀጣይ የማእከሉ የአገልግሎት አቅጣጫዎች ዙሪያ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።

"መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት" በሚል ርእስም በአባ ዘሚካኤል  በማኀበራዊ ሕይወት ዙሪያ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን ከመደበኛ የአገልግሎት ክንውን በተጨማሪም መንፈሳዊ ሕይወትን በሚመለከት የምክክር መርሐ ግብር ተከናውኗል፡፡

የገጽ ለገጽ ስብሰባ፥ የማእከሉ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት በአካል በመገናኘት ይበልጥ የሚተዋወቁበትና የሚወያዩት በዓመት አንድ ጊዜ የሚካሄድ ልዩ መርሐግብር ነው፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

11 Feb, 08:11


ከተለያዩ ወረዳ ማእከላት እና ግንኙነት ጣቢያዎች ለተውጣጡ የደረጃ አንድ ተተኪ መምህራን ሥልጠና መሰጠቱን በማኅበረ ቅዱሳን የአሶሳ ማእከል ገለጸ።

  የካቲት ፬/፳፻፲፯ ዓ. ም

ማኅበረ ቅዱሳን በአሶሳ ማእከል በስብከተ ወንጌልና በዜማ አገልግሎት ዋና ክፍል አዘጋጅነት ከወረዳ ማእከላት እና ከግንኙነት ጣቢያዎች ለተውጣጡ ከ26 በላይ ለሚሆኑ ሰባኪያነ ወንጌል የደረጃ አንድ ተተኪ መምህራን ሥልጠና በመንበረ ሠላም ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ሰበካ ጉባኤ አዳራሽ ውስጥ ከጥር 30 እስከ የካቲት 02/2017 ዓ.ም ድረስ ተሰጥቷል።

የማእከሉ  የስብከተ ወንጌልና የዜማ አገልግሎት ዋና ክፍል  አስተባባሪ ዲያቆን ወርቁ ጋሹ እንዳሉት የተሰጠው ሥልጠና በነገረ ሃይማኖት፣ነገረ ቅዱሳን ፣በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ፣ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ በክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር፣ በቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ በመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እንዲሁም በሐዋርያዊ ተልዕኮ ትምህርቶች ላይ ያተኮረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አስተባባሪው አክለውም ሥልጠናው ተተኪ ሰባኪያነ ወንጌልን ማፍራት፣ ምእመናን በአካባቢያቸው ቋንቋ ትምህርተ ወንጌልን አንዲማሩ እና ሠልጣኞች ባገኙት ዕውቀት አዳዲስ አማንያንን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች  እንዲያደርጉ ነው ብለዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

10 Feb, 17:54


ማኅበረ ቅዱሳን በወላይታ ማእከል  ለቅድመ ግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የጉዞ  መርሐ ግብር ማካሄዱ ተገለጸ፡፡

የካቲት ፫/፳፻፲፯ ዓ.ም


በወላይታ ሶዶ ከተማ በሚገኙት በግልና በመንግሥት ትምህርት ቤቶች የቅድመ ግቢ ጉባኤ ሥልጠና የሚከታተሉ ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች መንፈሳዊ የእግር ጉዞ ወደ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለሃይማኖት ገዳም የካቲት 1/ 2017 ዓ.ም አከናውነዋል፡፡

በጉዞም የሊቃ ፣የቆንቶ ልጃገረድ እና ጮራ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ኦርቶዶክሳዊያን ተማሪዎች  ተሳትፈዋል፡፡

በዕለቱ ከወላይታ ማእከል የተመደቡ የኦቶና ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ሰበካ ጉባኤ ዋና ጸሐፊ ዲ/ን አቤነዘር መስፍን “ልባም ሰው” ማቴ 7፡24 በሚል ርዕስ ትምህርተ ወንጌል የተሰጠ ሲሆን በተጨማሪም ከገዳማዊያን አባቶች  ምክር እና ቡራኬ ተሰጥቷል፡፡

መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን ወላይታ ማእከል  ሕ/ግ እና ሚዲያ ክፍል ነው

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

08 Feb, 20:16


ማኅበረ ቅዱሳን የግቢ ጉባኤያት ሥርዓተ ትምህርት የአሠልጣኞች ሥልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ ተገለጸ

የካቲት ፩/፳፻፲፯ ዓ.ም 

ማኅበረ ቅዱሳን በአዲሱ ግቢ ጉባኤያት ሥርዓተ ትምህርት የሙከራ ትግበራና ለማእከላት የአሠልጣኞች ሥልጠና በዛሬው ዕለት በማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል እየሠጠ እንደሚገኝ የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ማሥተባበሪያ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አበበ በዳዳ ገልጸዋል።

ለሥልጠናው ከ12 ማእከላት ማለትም (ባሕር ዳር፣ ጎንደር፣ ደብረ ብርሃን፣ አዲስ አበባ፣ አዳማ፣ ሐረር፣ ሚዛን፣ አርባ ምንጭ፣ አምቦ፣ ወልቂጤ፣ ሐዋሳና ባሌ ሮቤ) የተወጣጡ ሠልጣኞችን አያሠለጠነ ሲሆን ሥልጠናውን የሚሠጡት በሥርዓተ ትምህርት ዝግጅቱ ላይ በከፍተኛ ኃላፊነት ሲሰሩ የነበሩ ባለሙያዎች ናቸው ተብሏል።

የሥልጠናው ዋና ዓላማም አዲሱ ሥርዓተ ት/ት  ሙሉ ትግበራ ከመከናወኑ በፊት ከ 2013-2015 ዓ.ም ግምገማ በማድረግ ሥርዓተ ትምህርቱን ለመከለስ የተዘጋጀ ሲሆን ይህም ነባሩ ሥርዓተ ት/ት ላይ የነበሩ ጉድለቶችን ለማተካከል ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ተቋማዊ ለውጥ በግቢ ጉባኤያት ላይ በተጨማሪነት እንዲሠሩ ያሰባቸውን ተግባራዊ ለማድረግ፣ የሰንበት ት/ቤት ሥርዓተ ት/ት ከግቢ ጉባኤያት ጋር በት/ትና በይዘት የሚመሳሰለውን ለማስተካከል እንዲሁም ትምህርት ሚንስቴር የቀየረው  የት/ርትና የሥልጠና ፍኖተ ካርታ በግቢ ጉባኤያት ት/ት  ላይ ያለውን ተጽዕኖ ከግምት ያስገባ እና መፍትሔ የሚሰጥ ሥርዓተ ት/ት ለማዘጋጀት እንደሆነ ሥራ አሥፈጻሚው ተናግረዋል ።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

08 Feb, 20:16


አቶ አበበ አክለውም ከዚህ ቀደም የሙከራ ትግበራ ሥልጠና በበይነ መረብ (በቨርቹዋል) ሲሰጥ እንደነበር በመግለጽ በመስፈርት የተመረጡ ደረጃ አንድ ግቢ ጉባኤያት ያሉባቸው ማእከላት ተወካዮቻቸውን በመላክ መምህራንና አስተባባሪዎች በአካል ለሁለት ቀናት እየሠለጠኑ እንደሚቀጥሉ ጠቁመዋል።

ሠልጣኞቹ ከዚህ እንደተመለሱ በተመረጡት ግቢ ጉባኤያት ላይ ሥርዓተ ትምህርቱን እንዲተገብሩ፣ በየማእከላቱ እንዲያሠለጥኑና እንዲያስተምሩ ለማድረግ እንደሆነም በመግለጽ የሙከራ ትግበራውን ውጤት በመገምገም በሚቀጥለው ዓመት ለሁሉም ማእከላት ተግባራዊ እንደሚሆን ተጠቁሟል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

08 Feb, 04:08


  .#ዐውደ ስብከት  ሥር” # “በእንተ ጾም ”  በሚል ርእስ  ጾም ማለት ምን ማለት እንደሆነ ፣ጾም በብሉይ ኪዳን ፣ጾም በሐዲስ ኪዳን ፣የጾም አይነቶች ፣የጾም መሠረታዊ ጥቅሞች ፣ዐቢይ ጾምን የምንጾምበት ምክንያት  በስፋት  ታስነብባለች።
  #በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# “መኑ ይእቲ ዛቲ   ክፍል አንድ " በሚል ዐቢይ ርእስ  እመቤታችን ማን  እንደሆነች፣ የእመቤታችን ከሴቶች መለየት እንዴት እንደሆነ ፤በነገረ ድኅነት የእመቤታችን ድርሻ  የሊቃውንት መጽሐፍ በማጣቀስ ትምህርት ይሰጣል ።

    #ዐቢይ ጉዳይ  ዐምድ  ሥር  ደግሞ “# መከራው እንጂ ፣ለሞት ጣር እንዳይሆን እንሥራ" በሚል ርእስ  የመከራው ዶፍ መገለጫዎችና ማድረግ ያለብን ጉዳዮች በዝርዝር ያሳያል
   •  #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር  ደግሞ  "#የኦርቶዶክሳዊ ጋብቻ ትምህርት "በሚል ርእስ   ዐቢይ ርእስ  በመልአከ ሰላም  ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው  ስለ ምሥጢረ ተክሊል፣ጋብቻ እንዴት እንደተጀመረ፣የጋብቻ ዓላማው ፣ከመጀመሪያው ጋብቻ ምን እንማራለን? ጋብቻ ብዙኃኑ የሚመኘው ሲሆን እንደምኞቱ ጸሎቱ የደረሰለት ስእለቱ የሰመረለት ስንቱ ይሆን? በሚል ሰፊት ትምህርት  ታሰተምራለች።
   • #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#ቅዱስ አቡነ ኢየሱስ ሞዓ፣ወላዴ አእላፍ አበ ብዙኃን" በሚል ርእስ  ስለ ቅዱሱ መጠራት፣ አገልግሎት በስፋትታስቃኛለች ።
   •  #በነገዋ  ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ  ሥር “ መንፈሳውያን ማኅበራት ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን " በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ክፍል ፫   በሚል ርእስ በ፭ መቶ ክፍለ ዘመን፤በዘመነ ላስታና ድኅረ ላስታ ፣ መንፈሳውያን ማኅበራት ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን በ21ኛው ክ/ዘመን ፣መንፈሳውያን ማኅበራት በአሁኑ ዘመን የሚሉ ርእሶች ይዛለች ።
  #በኪነ ጥበብ ዐምድ "#ጥሪ_ክፍል _፪ "በሚል  ታስነብባለች ።
•  #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “የማዕረግ ስም አሰጣጥ # ክፍል ፩ " በሚል ርእስ #በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የሐዲስ ኪዳን የአንድምታ ትርጓሜ መምህር የሆኑትን #መጋቤ ሐዲስ ስቡሕ አዳምጤን ጋር የተደረገ  ጥያቄና መልስ ይዛለች።  ።
   ሐመር መጽሔት #፴፩ ኛ ዓመት   ቁጥር ፲፪ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !

magazine @eotcmk.org  #ሐመር #መጽሔት  ዝግጅት  ክፍል

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

08 Feb, 04:08


✍️✍️ሐመር መጽሔት በየካቲት ወር እትሟ!  
  ".. እጅግ ብዙ የመከራ ማዕበል ቢጎርፍም ሁልጊዜም አምላኳ ከእርሷ ጋር ስለሆነ ይገፏት ይሆናል እንጂ አትወድቅም "  የካቲት ዕትም በ፳፻፲፯ ዓ.ም መልእክት ዐምድ
 #የኅትመት ዘመን ፦#የካቲት ፳፻፲፯  ዓ.ም
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
•  ገጽ ብዛት፦፳፰
   ዋጋ ፦፵ ብር 
•  ሐመር  መጽሔት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት  ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል  በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡
•  ሐመር መጽሔት ፴፪ኛ ዓመት  ቁጥር ፪  # የካቲት ፳፻፲፯  ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " # ‹‹  #የአሕዛብን ስድብ አትሸከሚም ››  በሚል ጠንንካራ መልእክት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  ምእመናን የክፋት ጠማቂዎችን ሤራ በመታገስና በታላቅ ንቃት በመመልከት ትኩረታቸውን በበዓላቸው ላይ፣ ልባቸውንም ከአምላካቸው ጋር በማድረግ በዓሉን በሰላም እንዳሰለፋና ትንኮሳዎቹ ትዕግሥትን የሚፈታተኑ ቢሆንም ‹‹ራሳቸው አምጥተው፣ ራሳቸው በሚያሮጡ›› ተንኮለኞች ሤራ ላለመጠለፍ ያደረጉት ጥንቃቄ የሚያስመሰግን እንደነበረ ።
       በአጠቃላይ ሲታይ ግን እንዲህ ዓይነቱ የክፉዎች መዳፈር ለሀገርም፣ ለመንግሥትም፣ ለቤተ እምነቶች ግንኙነትም አይጠቅምም፡፡ ድፍረቱ ደግሞ በሰዎች ላይ ብቻ ሳይሆን ሁሉን በሚችል አምላክ ላይ የተፈጸመ ደፍረት በመሆኑ ሀገርና ወገንን የሚያስከፍለው  ዋጋ አሁን እየተቀበልን ካለው በላይ እንዳይሆን መጠንቀቅ  እንደሚገባ ሐመር በመልእክት ዐምድ ታስነብባለች።
   

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

07 Feb, 12:19


የግቢ ጉባኤያት ተቋማዊ ለውጥ ብቁ ዜጎችን በማፍራት ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ተገለጸ።

ጥር ፴/፳፻፲፯ ዓ.ም

በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎችን በግቢ ጉባኤያት ማዕቀፍ ውስጥ በማካተት ለቤተ ክርስቲያን ብሎም ለሀገር የሚጠቅሙ ዜጎችን ለማፍራት ማኀበረ ቅዱሳን ሥራዎችን እየሰራ ሲሆን አሁን ላይ ተቋማዊ ለውጥ ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል፡፡

በማኀበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ተቋማዊ ለውጥ ትግበራ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲያቆን ጌትነት መሠረት እንደገለጹት ተቋማዊ ለውጡ ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት ግቢ ጉባኤያቱ ከደረሱበት አሁናዊ ሁኔታና ከዓለም ዓቀፍ ሁነቶች አንጻር አገልግሎታቸውን በምን መልኩ መፈጸም እንደሚገባቸው ለማሳየት ነው ብለዋል፡፡

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎች ሙሉ ስብዕናቸውን የሚገነባ ትምህርቶችን በማስተማር ዘመኑን የዋጁ ምሉዕ ኦርቶዶክሳዊያን እንዲሆኑ : በቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መዋቅር ውስጥ እንዲሳተፉ : በማኀበራዊ፣በኢኮኖሚያዊና በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ እንዲያገለግሉ ለማድረግ የተቋማዊ ለውጡ ዓላማ ነው ሲሉ  በማኀበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ምክትል ሰብሳቢ አቶ በረከት መሠረት ገልጸዋል፡፡

መጋቤ ብርሃናት ቀሲስ ሙሉቀን ብርሃኑ በማኀበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል የግቢ ጉባኤያት አማካሪ ቦርድ ሰብሳቢ በበኩላቸው የግቢ ጉባኤያት ዓላማቸው ተተኪ ትውልድ ማፍራት ነው ያሉ ሲሆን ለውጡ እንዲሳካ ሁሉም የራሱን አስተዋፅዖ እንዲያበረክት አሳስበዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

06 Feb, 20:13


የአውስትራሊያ ማእከል  ገዳማትንና የአብነት ትምህርት ቤቶችን መደገፍ በሚቻልበት መልኩ  ውይይት ማድረጉ ተገለጸ።

ጥር ፳፱/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኀበረ ቅዱሳን በአውስትራሊያ ማእከል ከ10 የጽዋዕ ማኀበራት ጋር ገዳማትን እና የአብነት ትምህርት ቤቶችን መደገፍ በሚቻልበት መንገድ እንዲሁም የገዳማት ነባራዊ ሁኔታን አስመልክቶ በቨርችዋል(በበይነ መረብ)  የግንዛቤ ማስጨበጫ ዉይይት መካሄዱ ተገልጿል፡፡

አቶ ፍጹም መንገሻ የአውስትራሊያ ማእከል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ከማኀበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቆይታ እንደገለጹት የገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ተጨባጭ ሁኔታቸውን ለማሳወቅና ድጋፍ እንዲደረግላቸው ውይይቱ በመሠረታዊነት ተከናውኗል ብለዋል።

ኃላፊው አክለዉም በጦርነትና በድርቅ ምክንያት በከፍተኛ ችግር ያሉ በተለይም በሰሜኑና በምስራቅ የሚገኙ ገዳማትን ከጽዋዕ ማኀበራት ጋር በመሆን ድጋፉ ተደራሽ እንደሚደረግላቸው ተናግረዋል፡፡

ገዳማትና የአብነት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ እንዲያገኙ ሁሉም የቤተ ክርስቲያን ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ ጥሪያቸውን ያስተላለፉ ሲሆን በውይይቱ ላይ የተገኙት የማኀበራቱ ተወካዮች ለተግባሩ ቁርጠኛ መሆናቸው ተመላክቷል፡፡

ድጋፉ በሀገሪቱ በተለያዩ አካባቢዎች በጦርነትና በድርቅ ለተጎዱ ገዳማትንና አብነት ትምህርት ቤቶችን የሚያካትት መሆኑ ተጠቅሷል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

06 Feb, 18:14


አበሳውና ኃጢኣቱ ሲበዛ እግዚአብሔር እውነተኛ ዳኛ ነውና ወደ ዳኝነት ተግባሩ ይገባል፤ይህ ደግሞ በሰብአ ትካት በሰዶምና በጎሞራ ያስተላለፈውን ዳኝነት ያስታውሰናል፤ አሁን ያለንበት ዘመን ዓመተ ምሕረት በመሆኑ እግዚአብሔር ለጊዜው ቢታገሠንም በኃጢኣታችን የምንጠየቅበት ጊዜ አዘጋጅቶአል፤ ዛሬም ቢሆን የማናስተውለው ሆነን ካልሆነ በስተቀር እግዚአብሔር ተግሣጹን ማስተላለፍ አላቆምም፤ በምድራችን ላይ በምናደርሰው የተዛባ ተግባር በጐርፍ፣ በድርቅ፣ በመሬት መንቀጥቀጥና በአየር መዛባት እየገሠጸን እንደሆነ ማስተዋል አለብን፤
እግዚአብሔር ከጥንቱ ከጠዋቱ ጀምሮ ምድርን እንድንከባከባት፤ እንድናበጃት፣ እንድናጠብቃትና እንድናለማት አዞናል፤ ሆኖም ይህን ትእዛዙን ገሸሽ አድርገን በኬሜካልና በመርዛም ጋዝ ምድርን በመበከል፣ደንዋን በመመጠርና ራቁቷን በማስቀረት በምናደርገው ድርጊት አበሳ እየፈጸምን እንደሆነ ያወቅነው አይመስልም፤ በዚህም ምክንያት በጐርፍ፣ በድርቅ ለሰው ልጆች በማይመች የኣየር ፀባይ ወዘተ . . . ስጋት ውስጥ እየወደቅን ነው፤

   በሌላም በኩል በምናወሳስበው የአስተዳደር ርእዮትና መሳሳብ የእግዚአብሔር ገንዘብ የሆነውን ሕዝብ እርስ በርሱ እንዲጋጭና ያላስፈላጊ አደጋ ላይ እንድወድቅ እያደረግን ነው፤ በዚህም ጠንቅ ሰላም እየደፈረሰ፣ ፍቅርና አንድነት እየላላ የሃይማኖት ክብርና ልዕልና እየተነካ ራሳችንንም እየጐዳን ነው፤በዚህ ሁሉ ተግባራችን  እግዚአብሔርን እያሳዘንን ነው፤ ይህ ሊገባንና ሊቈረቁረን ይገባል፤
  የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት
ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው፤ መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው፤ ከእኛ በንስሓ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል፤ እግዚአብሔር ደግሞ ይህንን ዓይነቱ ንስሓ ከኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል፤በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል፤ ከዚህ አንጻር በአሁኑ ጊዜ ለሀገራችንና ለዓለማችን ስጋት የሆኑ የጦርነት ክሥተቶች፣ የመሬት መንቀጥቀጥ፣ የአየር መዛባት፣የድርቅ መከሠት፣የጎርፍ መጥለቅለቅ የሰላም መደፍረስ፣ የሰላማውያን ወገኖች መጎዳት፣ የፍቅርና የአንድነት መላላት ወዘተ. . . . ከምድራችን ተወግደው ፍጹም ምሕረትና ሰላም እናገኝ ዘንድ በኃጢኣታችን ተጸጽተን በምህላ ንስሓ መግባት አለብን፤ ከዚህ አኳያ ከጥንት ጀምሮ በቤተክርስቲያናችን ቀኖናዊ ሥርዓት መሠረት በየዓመቱ የሚጾመው ጾመ ነነዌ ለዚህ አመቺ ጊዜ ስለሆነ ከየካቲት ፫ ቀን ፳፻፲፯ ዓመተ ምሕረት ጀምሮ  ለሦስት ቀናት ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ሁላችንም ጠዋትና ማታ በየቤተክርስቲያኑ ዐውደ ምሕረት እየተገኘን በንስሓ በዕንባ በጸሎት በምህላ የእግዚአብሔርን ምሕረትና ይቅርታ እንድንጠይቅ፤ እንደዚሁም በሀገራችንና በውጭ ያላችሁ ሊቃውንተ ሕዝብ ቀኖናውን ጠብቃችሁ ይህንን በማስፈጸም ምህላውን በቀኖናው መሠረት እንድታከናውኑ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን፤
እግዚአብሔር አምላካችን ምሕረቱን ይቅርታውንና ሰላሙን ለሀገራችንና ለዓለማችን ይስጠን፤ ምህላችንንም ይቀበልልን፤
   “እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ” ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስምወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
ጥር ፳፱ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ምንጭ:- EOTC Broadcasting Service Agency

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

06 Feb, 18:14


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2017 ዓ.ም የጾመ ነነዌ የሰላምና የጸሎት አዋጅ መግለጫ
ሙሉ መልእክት የሚከተለው ነው፡፡

ጥር ፳፱/፳፻፲፯ዓ.ም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተላለፈ የምህላ ሱባዔ፡-
‹‹ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምህላ አስተጋብኡ ሕዝበ ሊቃውንተ ሕዝብ፤ ጾምን ቀድሱ፣ጉባኤውንም አውጁ፤ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ ኣምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፤ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ (ኢዩ ፩÷፲፬)
    ሁላችንም እንደምናውቀው ያለንበት ዓለም የመከራ ዓለም ነው፣ መከራው በኛ ስሕተትና ክፋት የመጣና እየሆነ ያለ መሆኑም ይታወቃል፤ እኛ የምንፈጽመው ጥቃቅንና ትላልቅ ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን እንደሚያስቈጣ በቅዱስ መጽሐፍ ተረጋግጦ ያደረ ነው፤ ለዚህም ከነነዌ ነዋሪ ሕዝብ የበለጠ ማስረጃ የለንም፤ የነነዌ ከተማ ነዋሪዎች በፈጸሙት ግብረ ኃጢአት እግዚአብሔርን አስቈጥተዋል፤ ድርጊታቸው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ ቢሆንም እሱ ምሕረቱን ማስቀደም ስለፈለገ በዮናስ በኩል አስጠንቅቆአቸዋል፤ የነነዌ ነዋሪዎችም በዮናስ በኩል የደረሳቸውን የንስሓ ጥሪ ወዲያውኑ ተቀብለው በምህላ፣ በጾም፣ በጸሎት ንስሓ ስለገቡ እግዚአብሔር ፍጹም ይቅርታ አድርጎላቸዋል፤
•  የተወደዳችሁ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያን ልጆቻችንና ወገኖቻችን !
እኛ ሰዎች ዛሬም በየሰዓቱ ብቻ ሳይሆን በየደቂቃው እግዚአብሔርን የሚያስቆጣ አበሳ እንደምንፈጽም ማወቅ ኣለብን፣

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

01 Feb, 17:35


ለልኀቀት ማእከሉ ግንባታ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት  ዝግጁ መሆናቸውን የአሜሪካ ማእከል አባላት አሳወቁ !!!

ማኅበሩ ባለ 14 ወለል የልኀቀት  ማእከል ግንባታ  ግንባታ መጀመሩንም ለአባላቱ አብስሯል:: በውይይቱ በመገኘት መልእክት ያስተላለፉት የማኅበረ ቅዱሳን  ሰብሳቢ አቶ ካሳሁን ኅ/ማርያም የማኅበሩ አገልግሎት እየዘመነ እና እየሰፋ በመሄዱ ተጨማሪ ሕንጻ ግንባታ ማከናወን እንዳስፈለገው አብራርተዋል :: በተጨማሪም የሚገነባው የልኀቀት  ማእከል የማኅበሩ አገልግሎት የደረሰበትን ጥልቀት እና ስፋት ከግምት በማስገባት የተጀመረ ሥራ መሆኑን አንስተው ሲጠናቀቅ ማኅበሩ ለቅድስት ቤተክርስቲያን የሚያበረክተውን ጉልህ አስተዋጽኦ የሚያግዝ ይሆናል ብለዋል::

የልኀቀት ማእከሉ ከመሬት በላይ 14 ወለል የሚኖሩት ሲሆን ከመሬት በታች ደግሞ 2 ወለሎች ይኖሩታል :: እስከ 1000 ሰው ድረስ የሚይዝ ግዙፍ መሰብሰቢያ አዳራሽ እስከ 40 ሰዎች የሚይዙ የተለያዩ መለስተኛ አዳራሾች እና ዘመናዊ የሚዲይ ስቱዲዮዎች በልኀቀት  ማእከሉ የሚካተቱ ናቸው። ለማኅበሩ አገልግሎት የሚሆኑ በርካታ ቢሮዎች እና በቂ የመኪና መቋሚያም የማእከሉ ግንባታ የሚያካትታቸው መሆኑ በውይይቱ ተገልጿል :: ይህን ማእከል ለመገንባት 4 መቶ ሚሊዮን ብር የሚያስፈልግ ሲሆን እስካሁን በተከናወነው ሥራ የከርሰ ምድር ቁፋሮን ጨምሮ ከመሬት በታች ያሉት ሥራዎች ተከናውነዋል ::

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

01 Feb, 17:35


የማኅበሩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መምህር ዋሲሁን በላይ ግንባታው  አሁን ያለበትን ደረጃና በዚህ ዓመት የተያዘውን እቅድ አስመልክቶ  ያቀረቡ ሲሆን በዚህ የቀጣይ የቤተክርስቲያን አገልግሎትን የሚያሳልጥ ማእከል ግንባታ የማኅበሩ አባላት እና የአገልግሎቱ ደጋፊዎች የበኩላቸውን በማድረግ የዚህ ታሪክ እንዲሆኑ ጠይቀዋል ::

የአሜሪካ ማእከል አባላትም በልኀቀት ማእከሉ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን አሻራ እንደሚያስቀምጡ በውይይቱ ላይ ቃል ገብተዋል።

ዘገባው የአሜሪካ ማእከል ሚዲያ ክፍል ነው።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

01 Feb, 11:59


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ  የግብጽ ኦርቶዶክስ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን ልዑካንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸው ተገለጸ፡፡

ጥር ፳፬/፳፻፲፯ ዓ.ም

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበ ተክለ ሃይማኖት የግብጽ ኮፕቲክ ቤተርክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ታውድሮስ ሁለተኛ መልእክት ይዘው የመጡትን ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን የነጋዳን፣ ጉስ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሚካኤል ገዳም ሓላፊን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ጥር ፳፬ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አነጋግረዋል፡፡

ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን ኮፕቲክ ቤተርክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ታውድሮስ ሁለተኛ ያመጡትን መልእክት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ያቀረቡ ሲሆን በዚህም  ቅዱስነታቸው የግብጽ ኮፕቲክ ልዑካንን ተቀብለው በማነጋገራቸው መደሰታቸውን ገልጸው፤ ይህም የሁለቱ አብያተ ክርስቲያናትን  አንድነት የሚያሳይ ነው ብለዋል ፡፡

በሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት መካከል ያለው ግንኙነት የጥንት መሆኑን ያስረዱት ሜትሮፖሊታን አምባ ቢመን “በግብጽ በርካታ ኢትዮጵያውያን ይኖራሉ፤ በዚያም ቤተክርስቲያን አላቸው ይጸልያሉ፡፡ የግብጽ ቤተክርስቲያን በኢትዮጵያ ለአማኞቿ አገልግሎት የምትሰጥበትን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  በጥሩ ሁኔታ ዕድሳት ተደርጎለት ተመርቆ ለአገልግሎት የሚጀምሩበትን ደብዳቤ ከቅዱስነታቸው መቀበላቸውን” አስረድተዋል፡፡

የሁለቱም አብያተ ክርስቲያንናት ግንኙነትም በጣም ጥሩ ነው ያሉት አቡነ ኤንገሎስ ኤልነጋዲ በኢትዮጵያ የግብጽ ቤተክርስቲያን ተወካይ እንደተናገሩት፤ በዚያም ቤተክርስቲያን አላቸው ይጸልያሉ፡፡ በኢትዮጵያም የግብጽ ቤተክርስቲያን አገልግሎቷን በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳምና በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ታካሂዳለች፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

01 Feb, 11:59


ካቴድራሉም ተጠናቆ ተመርቆ ለአገልግሎት በመብቃቱ በጣም ደስተኞች ነን ብለዋል፡፡ 

ልዑካኑ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ታዋድሮስ የግብጽ ኮፕቲክ ፓትርያርክ የተላከውን ስጦታ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስረከቡ ሲሆን ቅዱስነታቸውም ስለ ስጦታው አመስገነዋል። ልዑካኑም ስለተደረገላቸው መልካም አቀባበልና ይሁንታ መደሰታቸውን ገልጸዋል።

አያይዘውም የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በኢትዮጵያውያን ምእመናን ዕድሳቱ ተሠርቶ ማለቁ እጅግ ደስ እንዳሰኛቸው በመግለጽ የግብጽ ኮፕቲክ እንደተለመደው በካቴድራሉ መገልገል የሚችሉበት መንገድ ስለ ተመቻቸላቸው አመስገነዋል፡፡

ሜትሮፖሊታን በመጨረሻም ለኦርቶዶክሳውያን ምእመናን ባስተላለፉት መልእክት “ኢትዮጵያውያን በእምነታችሁ ጠንካራ ክርስቲያኖች ናችሁ፡፡ የሰይጣን ፈተና በመላው ዓለም ለምንኖር ክርስቲያኖች ቢሆንም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፤ ፈተናውን ያሳልፍልናል፡፡ በቤተክርስቲያን ሁናችሁ ጸልዩ" ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ምንጭ :- የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

27 Jan, 13:26


በሲዳማ ሀገረ ስብከት በሀዋሳ ከተማ የታነጸው የሀዋሳ አየር ማረፊያ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን ተመረቀ።

ጥር ፲፱/፳፻፲፯ ዓ.ም

በኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩኒቨርሲቲ ማኀበረሰብ፣በCAPAT ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የበረራ ሠራተኞች መንፈሳዊ ጉባኤ እና በማኅበረ ቅዱሳን አስተባባሪነት የታነጸው የሀዋሳ አየር ማረፊያ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቤተክርስቲያን በትናንትናው ዕለት ጥር 18 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቆ ቅዳሴ ቤቱ ተከብሮ ውሏል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ በክልል ትግራይ ደቡባዊ ዞን ማይጨው የደቡባዊ ምሥራቅ ትግራይ  አህጉረ ስብከት እና በመንበረ ፓትርያርክ የቅርሳ ቅርስ ቤተ መጻሕፍት ወመዘክር ሙዚየም መምሪያ የማኅበራት መምሪያ  የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ ፣መጋቤ ጥበባት ቀሲስ ሞላልኝ መርጊያ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅና የሀገረ ስብከቱ የመምሪያ ክፍል ኃላፊዎች፣መ/ፀ/መ/ር/ቆ/አባ ኪዳነማርያም የሀዋሳ ደ/ም/ቅ/ገብርኤል ገዳም አስተዳዳሪን ጨምሮ የሌሎች ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንደተናገሩት ይህ ቤተክርስቲያን የተሰራው የእግዚአብሔር ስም እንዲጠራበት እንዲሁም ምእመናን እንዲባረኩበት ነው ያሉ ሲሆን ለመጀመሪያ ጊዜም ታቦተ ሕጉ ወጥቶ በዓለ ንግሡም ተከብሯል፡፡

በተጨማሪም በቦታው በርካታ ቁጥር ያላቸው ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ውጭ የሆኑ ምእመናን በታደሙበት ለተግባሩ መሳካት አስተዋጽኦ ላደረጉ አካላት የምስጋና የምስክር ወረቀትና ስጦታዎች ተበርክቷል።

የተመረቀው ቤተ ክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ዮሴፍ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በሚያዝያ 05 ቀን 2016 ዓ.ም መሠረት ድንጋይ መቀመጡ ይታወሳል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

27 Jan, 13:26


“መከራ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እና ለእኛ  ለልጆቿ  አዲስ አይደለም!!”፡- ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ

ጥር ፲፱/፳፻፲፯ ዓ.ም

በማኅበረ ቅዱሳን የወልድያ ማእከል ሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት ለብፁዕ አቡነ ቄርሎስን የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጥር 17 ቀን 2017 ዓ.ም  የገና እና የጥምቀት በዓላትን ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደርሰዎ መርሐ ግብር አከናውነዋል።

ብፁዕነታቸው እንደተናገሩት “መከራ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም ለእኛ ለልጆቿ  አዲስ አይደለም” ስለዚህ  ሁላችሁም በመከራው ተስፋ ሳትቆርጡ በመጽናት የምትችሉትን ሥራ ሥሩ  በማለት የተናገሩ ሲሆን እንደ ማኅበርም አንድነታችሁን አጽኑ በማለት አባታዊ መመሪያ እና ቡራኬ ሰጥተው ስለጠየቃችሁኝ አመሠግናለሁ ብለዋል።

በተጨማሪነትም በመርሐ ግብሩ ላይ በማእከሉ መዘምራን መዝሙር የቀረበ ሲሆን  አጠቃላይ የማኅበሩን የሥራ እንቅስቃሴ እና የአባላትን ሁኔታ  ጠይቀዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

19 Jan, 18:34


በምእራብ አርሲ ሀገረ ስብከት በነንሰቦ ወረዳ
ገረምባሞ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ የጥምቀት በዓል ተከበሯል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

19 Jan, 18:34


በድሬዳዋ ከተማ ሁሉም ታቦታት በሰላም ወደ መንበረ ክብራቸው ገብተዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

19 Jan, 18:34


በአሜሪካን ሀገር የካንሳስ ደብረ ብርሃን ኪዳነ ምሕረት ወቅዱስ ሚካኤል እና የካንሳስ ደብር ሳህል መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን የጥምቀት በአልን በጋራ አከበሩ።
በዓሉን ለየት የሚደርገው ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት ከረጅም ዓመታት በኃላ ለመጀመርያ ጊዜ በአንድነት በጋራ አክብረዋል።
ምንም እንኳን የአየር ንብረቱ ቀዝቃዛ ቢሆንም ምእመናን ቅዝቃዜውን ተቋቁመው በቦታው በመገኘት እያከበሩት ይገኛሉ።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

10 Jan, 17:31


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ 
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት  ወቅታዊ  ጉዳዮችን አስመልክተው  አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

10 Jan, 12:17


በማኅበረ ቅዱሳን የጎንደር ማእከል “አደራ አለብኝ” በሚል መሪ ቃል መርሐ ግብር አከናወነ።

ጥር ፪ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም

“አደራ አለብኝ” በሚል መሪ ቃል የማኅበረ ቅዱሳን ጎንደር ማእከል ታኅሣሥ 27 ቀን 2017 ዓ.ም በማእከሉ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የድኅረ ግቢ ጉባኤ መርሐ ግብር ማካሄዱ ተገልጿል፡፡

በመርሐ ግብሩ ከ140 በላይ የግቢ ምሩቃን የተሳተፉ ሲሆን "የአገልግሎት በር" በሚል ርዕስ ሥልጠና ተሰጥቷል።

በተለያዩ የአገልግሎት ዘርፎች ለረዥም ጊዜ ያገለገሉ አባላት የልምድ ልውውጥ በማካፈል አባላት ሥራ፣ ሁኔታ፣ ቦታና ጊዜ ሳይገድባቸው ባሉበት ሆነው ሐዊርያዊ አገልግሎታቸውን መፈጸም እንደሚገባቸው መልእክት ተላልፏል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

09 Jan, 18:35


የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር ተከናወነ።

ጥር ፩ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በዓል የእንኳን አደረስዎ መርሐ ግብር በጽርሐ ተዋሕዶ ተካሂዷል።

በመርሐ-ግብሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየመምሪያ ኀላፊዎች የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ሠራተኞች የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች በጽሑፍ የተደገፈ የእንኳን አደረሰዎ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በዓሉን የተመለከተ ዝማሬ በሊቃውንት ቀርቧል።

ቅዱስ ፓትርያርኩም በመርሐ ግብሩ ለተገኙት እንግዶች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኃን አገልግሎት ስርጭት ድርጅት/EOTC

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

06 Jan, 08:41


https://youtu.be/bFhho368ocg?si=QDSp_oHTdUdmzAy5

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

06 Jan, 08:41


የደብረ ምሕረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ቅኔ ምስክር ጉባኤ ቤት ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ።

በማእከለዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የደብረ ምሕረት አቡን ቤት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የቅኔ ምስክር ጉባኤ ቤት 21 ደቀ መዛሙርትን ታኅሣሥ 27 ቀን 2017 ዓ.ም አስመርቋል ።

በመርሐ ግብሩ ላይ የማእከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ ፣የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ዮሴፍ ፣ ከተለያዮ ቦታዎች የመጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን ተግኝተዋል።

የቀዳሜ አድባራት አበራ ቅዱስ ጊዮርጊስ የቅኔ ምስክር መምህር ወላደ አእላፋት ጌድዎን አበበ ና ተመራቂ ደቀ መዛሙርቱ ቅኔ አቅርበዋል።

ብፁዕነታቸው ባስተላለፉ መልእክት ጉባኤ ቤቱ ያለበትን ችግር ተቋቁሞ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያፈራ በመሆኑ ትኩረት የሚፈልግ ጉባኤ ቤት ነው ብለዋል።

ጉባኤ ቤቱ የቦታ ጥበት እና ከከተማ በሚለቀቅ ፍሳሽ ከፍተኛ ችግር እየደረሰበት በመሆኑ በዘመናዊ መልኩ ለመገንባት የሕንጻ ዲዛይኑ ተሰርቶ መጠናቀቁም ተጠቁሟል።

በማኅበረ ቅዱሳን የጎንደር ማእከል ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ፍቃደ ፈጠነ በጉባኤ ቤቱ ዘርፈ ብዙ ችግሮች መኖሩን ጠቅሰው ግንባታው ተጀምሮ በታቀደለት ዕለት እንዲጠናቀቅ ከሀገር ውጭና በሀገር ውስጥ የሚኖሩ ምእመናን ተሳትፎ ያስፈልጋል ብለዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

05 Jan, 15:33


የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎትን ማጠናከር በሚቻልበት መንገድ ዙሪያ ምክክር ተደረገ።

ማኅበረ ቅዱሳን በስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዙሪያ እያከናወነ ያለውን ተግባር ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ዙሪያ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ከሚገኙ  ሰ/ት/ቤቶች ጋር ውይይት አድርጓል።

በጠረፋማ አካባቢዎች ያለውን የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ለማገዝ በተለያዩ ጊዜያት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ተተኪ መምህራንን በማስመጣት ሥልጠናዎችን ሲሰጡ እንደነበር ይታወቃል።

ማኅበረ ቅዱሳን በዚህ የአገልግሎት ዘርፍ ላይ ተሳትፎ እያደረጉ ከሚገኙ እና አገልግሎቱን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ካሉ ሰ/ት/ቤቶች ጋር በትናንትናው ዕለት በማኅበሩ ሕንጻ ላይ ውይይት አከናውኗል።

በውይይቱ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ኃላፊ የሆኑት አቶ ሰይፈ ዓለማየሁ እንደገለጹት የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ውጤታማ በሆነ መልኩ ለማከናወን ሁሉም አካላት በትብብር መሥራት ይገባቸዋል ብለዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዳይሬክተር የሆኑት ዲ/ን ሙሉጌታ ነጋ ለተሳታፊዎች በአገልግሎቱ ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን እስካሁን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥልጠና የተከታተሉ ተተኪ መምህራን በየአካባቢዎቻቸው የሠሯቸውን ተግባራት በሪፖርት መልክ አቅርበዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

05 Jan, 15:33


የማኅበሩ የዜማ እና ኪነ ጥበባት ማእከል ኃላፊ አቶ ፈቃዱ ምሕረቴ በበኩላቸው በጠረፋማ አካባቢዎች ለሚገኙ ምእመናን በቋንቋቸው ዝማሬዎችን ለማዳረስ ማኅበሩ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸው ሰ/ት/ቤቶች እና ማኅበራት በዚህ ተግባር ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ተሳታፊ የሆኑ ሰ/ት/ቤቶች የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ የሆነውን የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ለማጠናከር ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

04 Jan, 12:56


በደብረ ዘመዳ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም ለሚገኙ 80 የአብነት ተማሪዎች ድጋፍ ተደረገ።

ታኅሣሥ ፳፮/ ፳፻፲፯ ዓ.ም ማኅበረ ቅዱሳን

በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በራያ ቆቦ ወረዳ ስር ለምትገኘው ለደብረ ዘመዳ ቅድስት ማርያም አንድነት ገዳም ለሚገኙ 80 የቅዳሴ ጉባኤ ቤት ተማሪዎች የምግብ ቁሳቁስ በትናንትናው ዕለት ድጋፍ መደረጉ ተገልጿል።

በማኅበረ ቅዱሳን የወልድያ ማእከል የጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ መለሰ አያሌው እንደገለጹት  ማእከሉ ከኢትዮጵያ ውጭ ከሚገኙ በጎ ፍቃደኛ ምእመናን የሰበሰበውን  ድጋፍ ማድረጉን  የገለጹ ሲሆን አሁን ካለው የኑሮ ውድነት እና የሰላም እጦት አንጻር ጉባኤ ቤቶች አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመሆናቸው በተጠናከረ ሁኔታ ተጨማሪ ድጋፎች ሊደረጉ ይገባል ብለዋል።

በተመሳሳይም መሰል ድጋፍ በጋዞ ወረዳ ቤተ ክህነት ስር ለሚገኘው የዋሮ ቅዱስ ሚካኤል ለ30 የዜማ ጉባኤ ቤት የአብነት ተማሪዎችም ተበርክቷል በዚህም በአጠቃላይ ለሁለቱም ጉባኤ ቤቶች 170‚000 (ከአንድ መቶ ሰባ ሺ ብር በላይ ወጭ መደረጉን ተገልጿል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

03 Jan, 07:31


✍️ሐመር መጽሔት በጥር  ወር እትሟ!✍️
✍️".. እኛም ጥምቀትን እንፈልጋለን የሚሉ ምእመናን  ብዙ ናቸው ..) #ሐመር #መጽሔት  በጥር  በ፳፻፲፯ ዓ.ም መልእክት ዐምድ  ✍️      
                   ༺ ༻ 
  #የኅትመት ዘመን ፦#ጥር ፳፻፲፯  ዓ.ም
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ  ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
•  ገጽ ብዛት፦፳፰
   ዋጋ ፦፵ ብር 
•  ሐመር  መጽሔት  የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት  ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በልማት ተቋማት አስተዳደር  በመጽሔት ዝግጅት ክፍል በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡
•  ሐመር መጽሔት ፴፩ ኛ ዓመት  ቁጥር-፩    #ጥር  ፳፻፲፯  ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " #ጥምቀትን የተጠሙ ነፍሳት "በሚል ዐቢይ መልእክት
አገልግሎቱን ከሚፈልጉት ምእመናን ቍጥር ጋር ባለመጣጠኑ የተጠመቁትም  ምእመናን የሚያነሡት ጥያቄ  “አጠመቃችሁን ነገር ግን እግዚአብሔርን የምናመልክበት፣ ሥጋ ወደሙን የምንቀበልበት ቤተ ክርስቲያን የለንም፤ የሚያስተምሩን መምህራን፣ ቀድሰው የሚያቈርቡን ካህናትና ዲያቆናትም የሉንም” የሚለውን ነው።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

03 Jan, 07:31


በአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት ሥር የሚገኙ አንዳንድ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ለአብነት ያህል ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ትጉሃን ሰንበት ትምህርት ቤት፣ የዘነብ ወርቅ ደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ እና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የፈለገ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት፣ የቤተል ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ፍሬ ሃይማኖት ሰንበት ትምህርት ቤት እና እንደእነዚህ ያሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በቋንቋ የሚሰብኩ ሰባክያንን አገልግሎቱ ከሚፈለግበት አካባቢ እያስመጡ ያሠለጥናሉ፤ የአገልግሎት ተሞክሯቸውንም እያሳዩ ይገኛሉ። እነዚህ በጣት የሚቆጠሩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ይህን ከሠሩ ሁሉም ቢተባበሩ የተፈለገውን ውጤት ማምጣት ይቻላል። መልካም እየሠሩ ያሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶችን አብነት በማድረግ ሁሉ ለእንደዚህ ያለው ተግባር መረባረብ “እኛም መጠመቅ እንፈልጋለን” ብለው ጥሪ ለሚያቀርቡ ምእመናን የድርሻቸውን ምላሽ ማዘጋጀት ይጠበቅባቸዋል።
“እኛም መጠመቅ እንፈልጋለን፤ እኛም እንደ እናንተ ኦርቶዶክስ መሆን እንፈልጋለን” ብለው ለሚጣሩት ወገኖቻችን ፈጥኖ ከመድረስ አኳያ ያለውን ጫና (ተግዳሮት) ሁሉም የየድርሻውን ቢወጣ የእነዚህን ጥምቀትን የተጠሙ ነፍሳት ጥያቄዎችን በሚገባ መመለስ  እንደሚቻል ሐመር በመልእክት ዐምድ ታስነብባለች።
.#ዐውደ ስብከት  ሥር” # “ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል" በሚል ርእስ  ባልንጀራ የሚለውን ቃል ትርጉምና አከፋፈል ፣ከክፉ ባልንጀራ መራቅ አሰፈላጊ  እንደሆነና ክፋት ለሰው ልጅ የባሕርዩ  እንደአልሆነ ና ለማሳያ ያህል የተወሰኑትን በማንሳት ከክፉ ባልንጅርነት ተጠብቀን በመልካም ባልንጅረነት እንድንጠቀም መንገድ ታሳያለች ።
  #በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# “ቃል ሥጋ  ሆነ” (ዮሐ.፩፥፲፬)  ክፍል ሁለት  " በሚል ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው  ጌታ ለምን እንደተወለደ  በዝርዝር ተዳሶበታል።
#ዐቢይ ጉዳይ  ዐምድ  ሥር  ደግሞ “# የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ችግር በመፍታት ረገድ የምእመናን ድርሻ   " በሚል ርእስ  ዓለምን ሊሞላ በሚገባው የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ውስጥ ቦታ ሊጠባቸው አይገባም፡፡ ‹‹ክርስትናችሁን ጠብቁ፣ ሲሞላላችሁ ጸበል ረጭተን፣ አጥምቀን፣ አቊርበን እናስተናግዳችኋለን፤›› ብቻ ተብለው የሚገፉ፣ ዘልቀው የመጡ ብቻ ተጨንቀውም ቢሆን በአገልግሎቱ ውስጥ ብልጭ፣ ብልጭ እንዲሉ ብቻ ማድረግ ሕዝባውያን ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፍቅርና ቅርበት እንዲኖራቸው አያደርግም፡፡ ስለዚህ ከዚህ የተሻገረ ተሳትፎ እንደሚፈልጉ  ያሳያል።
በአፈጻጸም  ችግር ምእመናን የሰበካ ጉባኤ ተወካይ ሁነው ተመርጠው ግን ቢሮ አካባቢ ባሉት ሠራተኞች  ሥራው  ይያዝና የተመረጡ የሰበካ ጉባኤ አባላት አዝነው ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በዕውቀትና በሙያ ምንምአገልግሎት ሳይሰጡ ከተመረጡበት የፈቃድ አገልገሎት  እንደሚወጡ፤ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት  ቤተ ክርስቲያን አባላት የሆኑ ምእመናን በተወሰነ መልኩ በሰበካ ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ። ይሁን እንጂ ብዙ ጊዜ ለቍጥር መሙያ ያህል እንጂ በወሳኝነት ሚና ላይ ሲሳተፉ  ብዙ እንደማይታዩ ታስነብባለች ፡፡ሙሉውን ጥር ሐመር ያንብቡ !
•  #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር  ደግሞ  "#“ድኾችንና ጦም አዳሪዎችን…ጥራ” "በሚል ርእስ 
በርካታ ሰዎች ቤታቸው ፈርሶባቸው፣ ሀብት ንብረታቸው ተወስዶባቸው፣  ሲያበሉ ሲያጠጡ የነበሩ አሁን አብሉኝ አጠጡኝ የሚሉ ሆነው፣ እንግዳ ሲቀበሉ የነበሩት የሚቀበላቸው አጥተው በየመጠለያው ወድቀው፣ አንዳንዶች ደግሞ ያንኑም እያጡት  በችግር ላይ ችግር ተደራርቦባቸዋልና እንደነዚህ ያሉትን በፍቅር ማስተናገድ እጅግ የበለጠ ዋጋ  እንዳለው በአጽንዖት ታሰተምራለች።
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “#የስደተኞች መጠጊያ ጁባ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን " ክፍል ሁለት በሚል ርእስ  ከቅዱስ ሲኖዶስ ጋር ያለውን ግንኙነት ፣ ከሀገረ ስብከቱ ጋር ያለውን ግንኙነት ፣ በሀገር ውስጥ ካሉ ተቋማት ጋር ያለ ግንኙነት ፣የነበሩ ተግዳሮቶችን  ታስቃኛለች ።
•  #በነገዋ  ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ  ሥር “ መንፈሳውያን ማኅበራት ለነገዋ ቤተ ክርስቲያን" በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ክፍል ሁለት   በሚል ርእስ ስለ መንፈሳዊ ማኅበራት በዓለማውያን ዘንድ ፣ መንፈሳውያን ማኅበራት በቤተ ክርስቲያን ታሪክ፤ መንፈሳውያን ማኅበራት የአገልግሎት ተሳትፎ፤ በእኛ ዘመን ለጽዋ ማኅበር የሰጠነው ትርጉም መስተካከል እንዳለበት  በተለይም በአሁኑ ዘመን መልካም ማድረግ ከመቼውም ጊዜ በላይ በሚያስፈልግበት ወቅት ይህንን ብናደርግ ትርጉም  እንደሚኖረው  ሰፊ ጉዳይይዛለች።
#በኪነ ጥበብ ዐምድ "#ጥሪ" ክፍል -፩"በሚል የሴቶች አለባበስን  በተለይም ራቁታቸውን ስለሚሄዱ  ለመንፈሳዊ ሕይወት አጠራራችን እንደሚለያይ ታስነብባለች።
•  #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “በዐልና አከባበሩ- # ክፍል ፪ " በሚል ርእስ #“በዓልንና የበዓል  አከባበርን” በተመለከተ የሚነሡ ጥያቄዎችን መሠረት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ  ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የትምህርትና ማሠልጠኛ መምሪያ ዋና ኃላፊ የሆኑትን መጋቤ ሐዲስ ኀይለ እግዚእ አሰፋ ጋር የተደረገ የመጨረሻ   ጥያቄና መልስ ይዛለች  ። ለምሳሌ፦የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን በዓል አንድነትና ልዩነት ።፤የበዓል አከባበር እንዴት መሆን እንዳለበት ፤በዓል ማክራችን ለምን እንደሚጠቅመን ፣ባናከብርስ ምን እንደሚቀርብን፣በዓል አከባበር ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች ፤እነዚህን ችግሮች እንዴት መፍታት እንደሚቻል ከሊቁ ጋር የተደረገውን ምልልስ ይዛለች
   ሐመር መጽሔት #፴፪  ኛ ዓመት   ቁጥር ፩  በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !
magazine @eotcmk.org  #ሐመር #መጽሔት  ዝግጅት  ክፍል

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

02 Jan, 14:42


ለቡግና ወረዳ በድርቅ ለተጎዱ 600 ሕጻናትና ለ4 የጤና ተቋማት የማኅበረ ቅዱሳን ላልይበላ ወረዳ ማዕከል ድጋፍ አደረገ።

ታኅሣሥ ፳፬/ ፳፻፲፯ ዓ.ም ማኅበረ ቅዱሳን

በዛሬው ዕለት በማኅበረ ቅዱሳን ላልይበላ ወረዳ ማእከል በሀገር ዉስጥና በዉጭ ሀገር ከሚገኙ በጎ ፍቃደኞች የተገኘውን ከ3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት አስቸኳይ የዕለት ምግብ በሰሜን ወሎ ዞን ቡግና ወረዳ በድርቅ ለተጎዱ 600 ሕጻናትና ለ4 የጤና ተቋማት ድጋፍ አድርጓል።

መምህር አበበ ሰጥአርጌ የላልይበላ ወረዳ ማእከል የሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ክፍል ኃላፊ እንዳሉት በቡግና ወረዳ ከሚገኙት ቀበሌዎች መካከል በብርኮ ቀበሌ ለ250 ሕጻናት እና በጉልሀ ቀበሌ ለ350 ሕጻናት በአጠቃላይ ለ600 ሕጻናት የዕለት ምግብ ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል፡፡

በ4 የጤና ጣቢያዎች በሕክምና ላይ ለሚገኙ ሕጻናት አገልግሎት የሚዉል፣ ለአይና፣ለቅዱስ ሀርቤና ለቆብ እንዲሁም በርካታ ታካሚዎች በሚገኙበት የብርኮ ጤና ጣቢያ ድጋፍ መደረጉን መምህር አበበ ገልጸዋል፡፡

የላልይበላ ወረዳ ማእከልና የድጋፉ አስተባባሪ ግብረ ኃይል አባላት ድጋፍ ያበረከቱትን በሀገር ውስጥና በዉጭ ሀገር የሚገኙ በጎ ፍቃደኞችን በሕጻናቱና በጤና ተቋማቱ ስም አመስግነው አሁን በተከሰተዉ ድርቅ ምክንያት በርካታ ሕጻናት ከፍተኛ ለሆነ የጤና ችግርና ለሞት ተጋላጭ በመሆናቸው ሌሎች አካላት ተጨማሪ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

31 Dec, 13:08


በእቅበተ አእምሮ እና በቤተክርስቲያን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለወጣቶቾ እና ለጽዋዕ ማኅበራት ሥልጠና ተሰጠ።

በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት የዋድላ ወረዳ ቤተ ክህነት የኮን ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከዋድላ ወረዳ ቤተ ክህነትና ከማኅበረ ቅዱሳን ኮን ወረዳ ማእከል ጋር በመቀናጀት “እቅበተ አእምሮ” በሚል ርዕሠ ጉዳይ በተለያየ ዘርፍ ለተሰማሩ ወጣቶች እና ለጽዋዕ ማኅበራት ሥልጠና ተሰጥቷል።

ሥልጠናው በዋናነት ወጣቱ ራሱን ከመናፍቃን እንዲጠበቅ እና የጽዋዕ ማኅበራትም እምነታቸውን ብሎም ቤተክርስትያናቸውን ነቅተው እንዲጠብቁ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።

የሐዲስ ኪዳን መምህር የሆኑት መምህር ኪነ ጥበብ ጌታሁን እንደገለጹት “ወጣቱ እራሱን ከሀሰተኛ ትምህርት ጠብቆ የእግዚአብሐርን መንግስት ለመውረስ መዘጋጀት አለበት” ሲሉ ተናግረው የጽዋዕ ማኅበራትም ቤተክርስትያን አሁን ያለችበትን ፈተና ተረድተው ለተለየ አገልግሎት ራሳቸውን ማዘጋጀት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የማኅበረ ቅዱሳን ኮን ወረዳ ማእከል ሰብሳቢ አቶ ሻንበል አበራ በበኩላቸው ወጣቶች ሃይማኖታችውን አውቀው፤ቤተክርስትያናችውን እንዲጠብቁ አሳስበው የጽዋዕ ማኅበራትም ዘመኑን የዋጀ ትምህርትና የጽዋዕ መርሐ ግብር በማዘጋጀት አባላቶቻቸው የሥርአተ ቤተክርስቲያን አክባሪ መሆን ይጠበቅባቸዋል ብለዋል።

በሥልጠናው 134 ሠልጣኞች እንደተሳተፉ ታውቋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

30 Dec, 14:40


በማኅበረ ቅዱሳን የደሴ ወረዳ ማእከል “ወደ ቀደመው አገልግሎታችን እንመለስ!!” በሚል መሪ ቃል የአባላት የማነቀቂያ መርሐ ግብር ተካሄደ

በማኅበረ ቅዱሳን የደሴ ወረዳ ማእከል በትላንትናው ዕለት ታኅሣሥ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት አዳራሽ “ወደ ቀደመው አገልግሎታችን እንመለስ” በሚል መሪ ቃል የአባላት የማነቀቂያ መርሐ ግብር ተካሂዷል፡፡

በመድረኩም ከማኅበረ ቅዱሳን መሥራች ከነበሩት አባላት አንዱ መ/ታ ዶ/ር ይቻለዋል ጎሽሜ ስለ ማኅበረ ቅዱሳንና አገልግሎቱን አስመልክቶ ገለጻ ባደረጉበት ወቅት በፈቃደኝነት፣በቂ ጊዜ በመስጠት፣በዓላማ ጽናት፣በመንፈሳዊ ሕይወት በመጠንከር፣ አርዓያ በመሆን፣የሚከሰቱ ፈተናዎችን ለመቋቋም ዝግጁ በመሆንና በአገልግሎት የሚገኝ ዋጋን ተስፋ በማድረግ መንፈሳዊ ስራዎችን በመሥራት ማገልገል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

የደሴ ማእከል ጽ/ቤት ኃላፊ ዲያቆን ሞላ ንጉሥ በበኩላቸው አጠቃላይ ስለ ማኅበረ ቅዱሳን የአገልግሎት፣ ተቋማዊ እሴት የገለጹ ሲሆን አባላት ከመቼውም ጊዜ በላይ ማኅበሩን እና ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል መትጋት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡

በተጨማሪም በመርሐ ግብሩ ላይ የደሴ ማእከል እያከናወናቸው ስለሚገኙት ተግባራት፣ስላጋጠሙ ችግሮች፣ማኅበረ ቅዱሳን ስላደረገው ተቋማዊ ለውጥ እና በአባላት የአገልግሎት ተሳትፎ ዙሪያ ሐሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

30 Dec, 14:40


“የገና ስጦታ ለየኔታ” በሚል መሪ ቃል የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር መካሄዱ ተገለጸ

“የገና ስጦታ ለየኔታ” በሚል መሪ ቃል ለገዳማትና ለአብነት ትምህርት ቤቶች ማጠናከሪያና ማስፋፊያ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ታኅሣሥ 20 ቀን 2017 ዓ.ም በዮድ አብሲኒያ የባህል አዳራሽ ተካሄዷል።

በመርሐ ግብሩ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መምህር ዋሲሁን በላይ ና የማኅበረ ቅዱሳን ስራ አመራር አባል ቀሲስ ሙሉጌታ ስዩም (ዶ/ር) እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ምእመናን ተገኝተዋል።

ቀሲስ ዶ/ር ሙሉጌታ ሥዩም የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን “ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲወለድ የሩቅ ምስራቅ ሰዎች የእጅ መንሻ፣ እንሰሳት እስትንፋሳቸውን እንደሰጡ እኛም የእርሱን አስተምህሮ ላስቀጠሉልን ለገዳማትና ለአብነት ትምህርት ቤቶች ካለን ላይ ማካፈል ይጠበቅብናል” በማለት ገልጸዋል።

ህዳር 15 የተጀመረው የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት እስከ ታኅሣሥ 30 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይ የተገለጸ ሲሆን ምእመናን የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም ለገዳማትና ለአብነት ትምህርት ቤቶች ስጦታቸውን መለገስ እንደሚችሉ ተጠቁማል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

29 Dec, 17:24


ከሸካ፣ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት የተወጣጡ ደቀ መዛሙርት ተመረቁ

ማኅበረ ቅዱሳን ከደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ እና ገብረ ክርስቶስ ፈለገ ሰላም ሰ/ት/ቤት እና ከደብሩ አስተዳደር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከሸካ፣ ቤንች ሸኮ እና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት የተወጣጡ ደቀ መዛሙርትን አሠልጥኖ አስመርቋል።

ለአንድ ወር በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮዎች ዙሪያ ሥልጠና ሲወስዱ ለቆዩት ሠልጣኞች በዛሬው ዕለት ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት የምርቃት መርሐ ግብር ተከናውኗል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ የደብሩ ሰ/ት/ቤት የሠልጣኞችን የትራንስፖርት እና የምግብ ወጪ ከመሸፈን ጀምሮ የመኝታ እና የሕክምና አገልግሎቶች በሙሉ በማሟላት ሥልጠናው ያለምንም ችግር እንዲጠናቀቅ ከፍተኛ ጥረት ማድረጉ ተገልጿል።

የደብሩ አስተዳደር ጽ/ቤት ሥልጠናው እንዲከናወን ፈቃድ ከመሥጠት ጀምሮ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱም በመርሐ ግብሩ ላይ ተነግሯል።

የማኅበረ ቅዱሳን ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ቀሲስ ዶ/ር ሄኖክ ፍቅሬ እንደተናገሩት ማኅበረ ቅዱሳን ቤተክርስቲያን በስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎቶች የምታከናውነውን አገልግሎት ለማጠናከር የተለያዩ ፕሮጀክቶችን ቀርጾ ተግባራዊ እያደረገ ይገኛል ያሉ ሲሆን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የተለያዩ ሰ/ት/ቤቶች በዚህ አገልግሎት ላይ ከማኅበሩ ጋር በመተባበር እየሠሩ በመሆናቸው ከፍተኛ ውጤት እየተመዘገበ እንደሆነ ገልጸዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

29 Dec, 17:24


ምክትል ሰብሳቢው ጨምረው እንደገለጹት ማኅበረ ቅዱሳን ሠልጣኞቹን ከመመልመል ጀምሮ  መምህራን በመመደብ ተሳትፎ እንዳደረገ አንስተው  የደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊ እና ገብረ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ጽ/ቤት እና የፈለገ ሰላም ሰ/ት/ቤት ሥልጠናው በታቀደለት መልኩ እንዲጠናቀቅ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ለሠልጣኞቹ አባታዊ የአገልግሎት መመሪያ የሰጡት ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ  በጠረፋማ አካባቢ ያለውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት መደገፍ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚገኙ ሁሉም አካላት ኃላፊነት ሊሆን እንደሚገባው ገልጸው የደብሩ አስተዳደር እና ሰ/ት/ቤት ያከናወኑት ተግባር ሊበረታታ እንደሚገባ ተናግረዋል።

በመጨረሻም ሥልጠናውን ለተከታተሉ ተተኪ መምህራን የመጽሐፍ ቅዱስ እና የምስክር ወረቀት ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

03 Dec, 19:18


https://youtu.be/48VpDrn7n2Y?si=CoSaBR5by0LYPrN6

ገባሬ መንክራት  ሰማዕት ሰማዕት መርቆሬዎስ
ተራድአነ  በገሃድ ተራድአነ በገሃድ
አዝ......
ለአረማዊ ወጣት መድኃኒት የሆንከው
ከአራዊት ጠብቀህ ከሞት የታደግከው
ካለመኖር ወደመኖር የመለስከው
ተራዳን በሃይማኖት ሆነን ለደከምነው
አዝ....
ዛሬም በእኛ ዘመን እንደ ዑልያኖስ
ጣኦት የሚያመልኩ የወጡ  ከመንፈስ
ከርስት እንዳይለዩን እደር በእኛ መሐል
ጥበብ ኃይል ሁነን መርቆሬዎስ ኃያል
አዝ....
የሮማዊ ሰማዕት የጳጳሳት ደስታ
የእግዚአብሔር አገልጋይ የኢትዮጵያ አለኝታ
ከእስር ቤት ወጥቶ ሥዕልህ  በተአምር
ዑልያኖስን ገድሎ ተመለሰ በክብር
አዝማች....
የአብ ወዳጁ  የእግዚአብሔር  አገልጋይ
 ልመናችንን  አድርስ ወደአምላክ አዶናይ
  በሞት እንዳንጠፋ በሕይወት ጠብቀን
በአንተ ተማጽነናል  ኪዳንህን አምነን
አዝ.....

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

02 Dec, 08:02


“ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ” በሚል መሪ ቃል የአባላት የቃል ኪዳን ማጽኛ መርሐ ግብር ተካሄደ፡፡


በኢ/ኦ/ተ/ቤተ ክርስቲያን በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ወደ ቀደመ ነገር እንመለስ በሚል መሪ ቃል የአባላት የቃል ኪዳን ማደሻ መርሐ ግብር በደብረ ሰላም ቦሌ መድኃኔዓለም እና መጥምቀ መለኮት ቤተ ክርስቲያን በትላንትናው ዕለት አከናውኗል፡፡


በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን ጨምሮ የማኅበሩ የሥራ አመራር አባላት እና ከ2000 በላይ የአዲስ አበባ ማእከል አባላት ታድመዋል፡፡


በመርሐ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ማእከል ሰብሳቢ ዲ/ን ኃ/ማርያም መድኅን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ሲያስተላልፉ  “ አዲስ አበባ ማእከል በተቋማዊ ለውጡ ትግበራ መሠረት የጀመረውን አዲሱን መዋቅራዊ አደረጃጀት ውጤታማ ለማድረግ ቀዳሚው ተግባር የአባላትን አገልግሎት ማጠናከር ነው” ብለዋል፡፡  ቀጥለውም “ አባላት ቃል ኪዳናቸውን አድሰው የአገልግሎት ተሳትፏቸውን እንዲያጠናክሩ እና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ወደ ማኅበሩ ሲቀላቀሉ የገቡትን ቃል ሊፈጽሙ ይገባል “ ሲሉ የአጽንዖት መልዕክታቸውን አስተላለፍዋል፡፡


የአባላት ተቋማዊ ለውጥ ትግበራ ዐቢይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዲ/ን ሲሳይ ብርሃኑ በዕለቱ ለተገኙ ታዳሚዎች ስለ ጉባኤው ዓላማ እና የአባላት ድርሻን በተመለከተ “የአባላት የአገልግሎት በር” በሚል ርዕስ ጽሑፍ ያቀረቡ ሲሆን አባላት በተቋማዊ ለውጥ ትግበራ ተሳትፏቸው የጎላ እንዲሆን የሚሳተፉባቸው የአገልግሎት አማራጭ በሮች ክፍት ሁነው እንደሚጠብቋቸውና ገብተው እንዲያገለግሉ አማራጭ የአገልግሎት በሮችን በዝርዝር አስረድተዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

02 Dec, 08:02


በዚሁ የአባላት ልዩ መርሐ ግብር ላይ በመ/ር ብርሃኑ አድማስ " እግዚአብሔርን ማየት" በሚል ትምህርተ ወንጌል፣ በቀ/ዶ/ር ይቻለዋል ጎሽሜ የማኅበረ ቅዱሳን የአገልግሎት ፈተናዎችና ጉዞን በተመለከተ ልምድ የማካፈል እና  በቀሲስ ዘማሪ ምንዳዬ ብርሃኑ እና በዘማሪት ብዙዓየሁ ተክሉ የመዝሙር  መርሐ ግብራት ተከናውነዋል፡፡


በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምዕራብ ካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አማካኝነት “እርፍ ይዞ ወደ ኋላ የለም፣ ማኅበራችሁን ጠብቁ ፣በገባችሁት ቃል መሠረት ቤተ ክርስቲያናችሁን አገልግሉ፡፡” በሚል አባታዊ ቡራኬ እና ቃለ ምዕዳን መርሐ ግብሩ ተጠናቋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

30 Nov, 10:48


"ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ"

ልዩ የአባላት የቃል ኪዳን ማጽኛ መርሐ ግብር


በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት በሙሉ የተዘጋጀ ልዩ የአገልግሎት ቃል ኪዳን ማጽኛ  መርሐ ግብር

እርስዎም በማኅበሩ ምሥረታ ጀምሮ በየትኛውም ወቅት በአባልነት ሲሳተፉ ከነበሩ በዚህ መርሐ ግብር ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።

ቀን፡ ኅዳር 22/2017 ዓ.ም
ሰዓት፡ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ
ቦታ፡ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም እና መጥምቁ ዮሐንስ ካቴድራል አዳራሽ

ለተጨማሪ መረጃ፡- 0911898990

"ወደ ሁሉም አቅጣጫ መመለሻ ትራስፖርት ተዘጋጅቷል"

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

29 Nov, 11:36


ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብን ማጠናከርና ማብቃትን መሠረት ያደረጉ የአመካካሪዎች ሥልጠና በተለያዩ ቦታዎች መሠጠታቸው ተገለጸ ።

የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት በሥልታዊ ዕቅዱ ትኩረት አድርጎ ከሚሠራባቸው አገልግሎቶች አንዱ በመንፈሳዊ የምክክር አገልግሎት የሚሰማሩ ካህናትና ባለሙያዎችን በማሠልጠንና በበቂ ሁኔታ በማዘጋጀት ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ የሚያጠናክሩ አካላትን ማፍራት አንዱ ነው።

በዚሁ መሠረት ከኅዳር 14 እስከ 15 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በወልቂጤ ማእከል አስተባባሪነት በጉራጌ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና አዳራሽ በተሰጠው ሥልጠና ከጉራጌና ምሥራቅ ጉራጌ አህጉረ ስብከት የተውጣጡ 31 ካህናት፣ ዲያቆንት፣ መምህራን፣ የሥነ-ልቦናና ሌሎች ባለሙያዎች ተሳትፈውበታል፡፡

በዚህ ሥልጠና ክብረ ክህነትና አበ ነፍስ፣ መንፈሳዊ የምክክር አገልግሎት አሰጣጥ፣ ኦርቶዶክሳዊ ጋብቻና የልጆች አስተዳደግ፣ የሱስ ችግሮችን ለማቃለል በኦርቶቶዶክሳዊ አስተምህሮ ዕይታ እንዲሁም ምጣኔ ሐብትና ማኅበራዊ ዕድገት ጉዳዮች ተዳሰውበታል፡፡
በወልቂጤ ከተማ በተሠጠው ሥልጠና ብፁዕ አቡነ መልከጸዴቅ የጉራጌ ሀገረ ስብከት እና የቅዱስ አቡነ ዜና ማርቆስ መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራችና የበላይ ጠባቂ ሊቀ ጳጳስ በቦታው በመገኘት ሥልጠናውን በጸሎት በመክፈት የሥራ መመሪያ የሰጡ ሲሆን፣ ሠልጣኞች ባገኙት ሥልጠና በመታገዝ ዘመኑን የዋጀ የቅድስት ቤተክርስቲያን ሁለንተናዊ አገልግሎት መስጠት እንዳለባቸው መልእክት አስተላልፈዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

29 Nov, 11:36


በተመሳሳይ ጊዜና ርእሰ ጉዳይ በሰቆጣ ማእከል በተሰጠው ሥልጠናም 43 ያህል ካህናት፣ መምህራንና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በእነዚህ ሥልጠናዎች የተሳተፉ ሠልጣኞች በሥልጠናው ጥሩ ግንዛቤና ልምድ እንዳገኙበት ገልጸው ወደ መጡበት አካባቢ ሲመለሱ ምእመናን ያለባቸውን ዘርፈ ብዙ ማኅበራዊ ቀውስ እንዲቋቋሙ የበኩላቸውን ድርሻ ለመወጣት እንደሚያስችላቸው ተናግረዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ለሥልጠናው መሳካት ቦታ አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ጭምር ለተባበሩት የጉራጌ ሀገረ ስብከትና ማእከላትን እያመሰገነ ቀጣይ በሌሎች አካባቢዎች ለሚሰጠው ሥልጠናም በገንዘብና ቁሳቁስ ጭምር በመደገፍ የቤተ ክርስቲያን አካላት በቅንጅት አብረው እንዲሠሩ ጥሪውን ያቀርባል፡፡
ይህን የሥልጠና መርሐ ግብር በገንዘብ መደገፍ ለምትፈልጉም፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400 መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

27 Nov, 04:32


የማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮች

ቴሌግራም፡- http://t.me/mkpublicrelation

የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት፡- http://www.facebook.com/eotcmkidusan/

የማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነት:-https://www.facebook.com/mahiberekidusan.mkusa/

ኢንስታግራም፡-  http://www.instagram.com/pr.deputy/

ድረገጽ፡- http://www.eotcmk.org

ትዊተር፡- http://www.twitter.com/@kidusanpr/

ዩ ቲዩብ፡- http://www.youtube.com/user/EOTCMK

https://www.youtube.com/@-zemawetibebzmk7905

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

25 Nov, 10:33


ሐመረ ብርሃን የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት የምስጋና መርሐ ግብር አካሄደ፡፡

የቀደመ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ጥበብና ዕውቀት ለማስፋፋት እየሠራ የሚገኘው የብራና መጻሕፍት ሥራ ድርጅት ለነበረው ስኬታማ ጉዞ ጉልህ ሚና የነበራቸው ባለ ድርሻ አካላትን የሚያመሰግንበት መርሐ ግብር ነው ያካሄደው፡፡

በመርሐ ግብሩም ላይ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕርዳርና ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሊቃውንት ጉባኤ ሰብሳቢ አቡነ እንድርያስ ፣ የዴንቨርና እና ኮሎራዶ አካባቢ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ተገኝተዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

25 Nov, 10:33


በዕለቱ  የመንበረ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ የጓንቻ ገዳም አቡነ ተጠምቀ መድኅን ገዳም ፣ደብረ ድማኅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ፤ ማኅበረ ቅዱሳን እና ሌሎች ማኅበራት እንዲሁም ተቋማት በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እጅ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የሐመረ ብርሃን የብራና የመጽሐፍት ሥራ ድርጅት የብራና ፣ የዕደ ጥበብ፣የስዕል፣የሕጻናት የአብነት ትምሕርት እና በሌሎቹም ዘርፍች በርካታ ሥራዎች እየሠራ የሚገኝ ሲሆን ከ5 በላይ ቅርንጫፎች ከፍቶ እየሠራ የሚገኝ መሆኑም ተገልጿል።

ድርጅቱ ከንጹሕ ምንጭ በተቀዳ ዕውቀትና ጥበብ ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላትና የተግባረ ዕድ ሥራዎችን እየሠራ የሚገኝ ሲሆን በ2010 ዓ.ም በ10 አገልጋዮች የተጀመረው የሐመረ ብርሃን የብራናና የመጽሐፍ ሥራ ድርጅት ከቤተ ክርስቲያን ጎን ለጎን ከመንግሥት አካላት ጋር እንደሚሠራም ተገልጿል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በሕጻናት የትምህርት መርሐ ግብር ሥነ ምግባርን ከዕውቀት ጋር የተዋሐዱለት ትውልድ በመፍጠር  ረገድ የበኩሉን ድርሻ እየተወጣ የሚገኝ ድርጅት መሆኑ ተጠቅሷል።

በመርሐ ግብሩ መልእክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ አብርሃም የብራና ዝግጅት ረጅም ጊዜ የሚወስድ በመሆኑ እየተዳከመ የመጣ ቢሆንም ዛሬ ላይ በዚህ መልክ እያደገ መምጣቱ የሚያስደስት ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ብፁዕነታቸው አባቶቻችን በድካም ያቆዩልንን ትውፊትና ታሪክ አንዱም ሳይዛባ እንዲቀጥል አጥብቃችሁ ያዙ ሲሉም አባታዊ ምክርና መመሪያ ሰጥተዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

20 Nov, 09:26


https://vm.tiktok.com/ZMhWYpoFv/

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

15 Nov, 09:22


ደብረ ቁስቋም

ኅዳር ፮ ቀን የአርያም ንግሥት፣ የፍጥረታት ሁሉ እመቤት፣ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ አረጋዊ ቅዱስ ዮሴፍንና ቅድስት ሰሎሜን አስከትላ ለ3 ዓመታት ከ6 ወራት የስደት እና የመከራ ዓመታት በኋላ በስተደቡብ የምትገኘው ደብረ ቁስቋም ላይ ያረፉችበት ዕለት ይከበራል፡፡

ደብረ ቁስቋም በደቡብ ግብጽ የሚገኝ ተራራ ነው፡፡ ይህ ተራራ የተቀደሰ ተራራ ስለመሆኑ የእስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ ታኦፊሎጎስ በድርሳነ ማርያም ‹‹ይህም ከሀገሮቹ ሁሉ ተራሮች የሚበልጥ (የተለየ) ከፍ ያለ ተራራ ነው፡፡ በውስጡ ቅዱስ አግዚአብሔር ያድራል፡፡ ይህንን ተራራ የእግዚአብሔር ልጅ ወዶታል፤ አክብሮታልምና፤ ከዓለም ሀገሮች ሁሉ ከተቀደሰች እናቱ ጋር አድሮባታልና፡፡ ከመላእክት ቤት ያድር ዘንድ አልወደደም፤ ቢታንያንም አልመረጠም፡፡ ከተራራው ላይ ባለች ገዳም ቤት ውስጥ አደረ እንጂ፤ ነቢዩ ዳዊት የጽዮንን ተራራ ወደደ፤ በአርያምም መቅደሱን ሠራ እንዳለ፡፡››

በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ለአረጋዊው ዮሴፍ በሕልሙ ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ግብጽ ሽሽ›› ባለው መሠረት የተፈጸመ ነው፡፡ (ማቴ. ፪፥፲፫-፲፭)

በስደቱም ጣዖታተ ግብጽ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በእነርሱም አድረው ሰውን ሲያስቱ የነበሩ አጋንንትም ሲሸሹ ታይተዋል፤ ደግሞም ጌታችን ዳግማዊ አዳም ነውና በምክረ ከይሲ (ዲያብሎስ) ምክንያት ተሰዶ የነበረው ቀዳማዊ አዳምን ለመካስ ተሰደደ፤ በዚህም አጋንንትን ከሰው ልቡና አውጥቶ አሳደደ፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

15 Nov, 09:22


እመቤታችን ቅድስት ማርያም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር ከመሰደዷ አስቀድሞ ነቢዩ ኢሳይያስ ‹‹ወይወርድ እግዚእነ ውስተ ምድረ ግብጽ እንዘ ይጼዐን ዲበ ደመና ቀሊል፤ ጌታችን በፈጣን ደመና (በእመቤታችን ጀርባ) ተጭኖ ወደ ግብጽ ይወርዳል›› ተብሎም በተናገረው መሠረት ትንቢቱ ተፈጽሟል፡፡ (ኢሳ. ፲፱፥፩)

ጌታችን ኢየሱስ  በደብረ ቁስቋም ቅዱሳን ሐዋርያቱን ሰበሰባቸው፤ታቦትንና ቤተ ክርስቲያንንም አክብሮ የቁርባን መሥዋዕትንም ሠርቶ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ሰጥቷቸዋል፡፡

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ከጌታችን ኢየሱስ ጋር በቁስቋም ተራራ ስድስት ወራትን ያረፈች ሲሆን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኅዳር ፮  የእነርሱን ስደትና ወደ ሀገራቸው እስራኤል መመለሳቸውን በማስታወስ ታከብራለች፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!!!

ምንጭ፤ ድርሳነ ማርያም (ትርጉም ፳፻፫ ዓ.ም)
              ስንክሳር ዘወርኃ ኅዳር

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

14 Nov, 17:14


"ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ"

ልዩ የአባላት የቃል ኪዳን ማደሻ መርሐ ግብር


በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የማኅበረ ቅዱሳን አባላት በሙሉ የተዘጋጀ ልዩ የአገልግሎት ቃል ኪዳን ማደሻ መርሐ ግብር

በዕለቱም፦

👉 የአባላት ተቋማዊ ለውጥ ትግበራ ማስጀመሪያ ልዩ መርሐ ግብር ይካሄዳል
👉 የማኅበሩ የአገልግሎት ሂደት በታላላቅ ወንድሞችና እኅቶች ይቀርባል
👉 በተቋማዊ ለውጡ ለአባላት የተዘጋጁ የአገልግሎት አማራጮች ጥናት ይቀርባል
👉 አባላት የአገልግሎት ቃል ኪዳናቸውን ያድሳሉ
👉 እንዲሁም ሌሎች ከአባላት ጋር የተያያዙ መርሐ ግብራት ይከናወናሉ።

እርስዎም ከማኅበሩ ምሥረታ ጀምሮ በየትኛውም ወቅት በአባልነት ሲሳተፉ ከነበሩ በዚህ መርሐ ግብር ላይ እንዲገኙ ተጋብዘዋል።

መረጃውን ለሌሎች አባላት በማጋራት የአገልግሎት ግዴታዎን ይወጡ!

ቀን፡ ኅዳር 22/2017 ዓ.ም
ሰዓት፡ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ
ቦታ፡ በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም እና መጥምቁ ዮሐንስ ካቴድራል አዳራሽ

ለተጨማሪ መረጃ፡- 0911898990

"ወደ ቀደመው ነገር እንመለስ"

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

13 Nov, 14:40


" ..በዚህ ወቅት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ በስፋት የሚሰማውን ብልሹ አሠራር ማረምና ለቀጣዩ አገልግሎት መልክ ማስያዝ የካህናቱ ትልቅ ድርሻ ነው፡ ፡ ፡"#ሐመር መጽሔት
ሐመር መጽሔት #የኀዳር ወር ዕትም በሁሉም የማኅበሩ ሱቆች ትገኛለች
༺ ༻
#የኅትመት ዘመን ፦#ኀዳር ፳፻፲፯ ዓ.ም ቁ.፲ ፩
#አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማኀበረ ቅዱሳን በልማት ተቋማት አስተዳደር በመጽሔት ዝግጅት ክፍል #በየወሩ የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት
• ገጽ ብዛት፦፳፰
ዋጋ ፦፵ ብር
• ሐመር መጽሔት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በልማት ተቋማት አስተዳደር በመጽሔት ዝግጅት ክፍል በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

13 Nov, 14:40


• ሐመር መጽሔት ፴፩ ኛ ዓመት ቁጥር -፲፩ ኀዳር ፳፻፲፯ ዓ.ም በመልዕክት ዐምድ “#እናንተ ግን የሌቦችና የቀማኞች ዋሻ አደረጋችሁት፤” በሚል ዐቢይ ርእስ በሁሉም መስክ ከወሬ ባለፈ ብልሹ አሠራርንና ዘረኝነትን በተግባር የሚፀየፍ አገልጋይ በታሰበው መጠንና ፍጥነት መፍጠር እንዳልተቻለ ፤በተቀደሰው ሥፍራ የጥፋት ርኵሰትን ማከናወን ሊቋቋሙት የማይችሉትን የእግዚአብሔር ቍጣ በራስ ላይ መጥራት ነው።
ሲገሠጹም ከመመለስ ይልቅ ለምን ታወቀብኝ ብሎ ሌላ በደል ለመጨመር መሯሯጣቸውና የእግዚአብሔርን ትዕግሥት መፈታተን መሆኑን አለመረዳታቸው ደግሞ ሌላው ጉዳይ እንደሆነ ፤ ችግር ዳር ሆኖ በማውራት፣ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ በማንሸራሸር፣ ከንፈር በመምጠጥና በተናጠልም እዚህም እዚያም በማለት የሚፈታ እንዳልሆነ ልንገነዘብና ሁላችንም ተገቢውን ሥራ ልንሠራ እንደሚገባ ፤ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ለአጥፊዎች መከታ፣ ሽፋንና ዋሻ የሆኑ አካላትም ከእነርሱ ጋር ከተሳሰሩበት ምድራዊ ማሰሪያ ይልቅ አባታቸው እግዚአብሔርና እናታቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደምትበልጥባቸው አስታውሰው አካሄዳቸውን በማስተካከል ከእውነት ጐን እንዲቆሙ ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
. #ዐውደ ስብከት ሥር ‹‹ወዳጄ በእሾህ መካከል እንዳለ የሱፍ አበባ ነሽ››(መኃ.፪፥፪) በሚልርእስ ከመዝሙራት ሁሉ በሚበልጥ መዝሙሩ ጠቢቡ ሰሎሞን በመንፈሰ ትንቢት ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ቅዱሳን ጻድቃን ስለ እውነተኞቹ ምእመናን (ክርስቲያኖች)፣ ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክብር ወዘተ. የተናገረው ነው፡፡ ጠቢቡ ሰሎሞን ትንቢቱን ምሳሌያዊ በሆነ አነጋገር ተናግሮታል፡ መሆኑን ያሳያል።
#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “#ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ (ዕብ.፲፫፥፰)" በሚል ዐቢይ ርእስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ክርስቶስን በኦሪት፣በነቢያት ፣በወንጌል፣ እንዴት እንደምስብከው ሰፊ ትምህርት ይሰጣል፡፡ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በሥርዓተ አምልኮቷ የክርስቶስን የባሕርይ አምላክነት በልዩ ልዩ መልኩ ታስረዳለች።
በሥርዓተ ቅዳሴዋ ውስጥ ቤተ ክርስቲያን ክርስቶስን እንደምትሰብከው ሁሉ ሥርዓተ ቅዳሴዋን እና ማኅሌት በምትፈጽምባቸው ንዋየ ቅድሳትም ትሰብከዋለች ።ቤተ ክርስቲያንን ሳያውቋት ሰዎች ስሟን እንዲሁ እናጠፋለን ብለው የሚያስቡበትን ልቡናቸውን ሽህ ጊዜ እንደገና መልሰው መላልሰው ሊያስቡበት ይገባል ። ይህን ሁሉ ቤተክርስቲያን ስታስተምር እየታየች ቤተ ክርስቲያን ስለ ክርስቶስ አታስተምርም ማለት ባላዩት ምስክር መሆን፤ ለራሱ ሳያውቅ እኔ ላሳውቅህ ማለትና ከአንተ ይልቅ እኔ ስለ አንተ አዋቂ ነኝ እንደ ማለት ይቆጠራል፡፡
#ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “‹‹ወይሠረዉ መፍቀርያነ ወርቅ፤ ወርቅን የሚወዱ ይነቀሉ›› (ቅዳሴ እግዚእ ቁ.፭) በሚል ዐቢይ ርእስ የወቅቱ የቤተ ክህነታችን ፈተና በጥልቀት ትዳስሳለች ።በአሁኑ ዘመን አንዳንድ የቅድስት ቤተክርስቲያን ባለሥልጣናት እንደ መንፈሳዊ መሪነት ሚናቸውን መወጣት ተስኗቸው እንደሚታዩ በመረጃ ትሞግታለች፡፡አንዳንድ የቅድስት ቤተክርስቲያን መሪዎች ብዙውን ጊዜ ከእግዚአብሔር አገልጋይነት ይልቅ እንደ ምድራዊ ምንደኛ፣ እንደ ፖለቲከኛ፣ እንደ ቢዝነስ ሰው ያለ የአካሄድ ዝንባሌን የሚያሳዩም መኖራቸውን ትጠቁማለች፡፡
በተለይ ገንዘብን በመሰብሰብና በማከማቸት ጥማት የታወሩትን ዛሬ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፈተና ሆነውብኛል ብላ እስከ ማወጅ ደርሳለች፡፡-አንዳንድ የቤተ ክህነቱ ባለሥልጣናት የቅድስት ቤተክርስቲያን የመንፈሳዊ ኃላፊነት ቦታዎችን፣ የአገልጋዮችን ቦታ ገንዘብ ለሚሹ ሰዎች በገንዘብ የሚሸጡ እየተበራከቱ እንደሆነ በመረጃ ትሞግታለች፡፡-በቅድስት ቤተ ክርስቲያን የአገልግሎት መደቦችንና የክህነትን ሥልጣን እንደ ቢዝነስ የሥራ መደቦችን የመሸጥ እና የመግዛት አካሄድ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በእጅጉ እየፈተናት ነው፡፡
የካህናት ቅጥርና ዝውውር፣ ስእለትና የምጽዋት ገንዘብ አስተዳደር፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰበሰበችው ገንዘብ የምታውልበት ዓላማ፣ የጥቂት አገልጋዮች ማካበት የብዙ አገልጋይ ካህናት መጎስቆል፣ የገንዘቡ አወጣጥና አገባብ፣ በግንባታ ሥራዎች ላይ ያለው የግዢና የገንዘብ አወጣጥ ሥርዓት የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የኪራይ ቤቶች አስተዳደር፣ምእመናን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ማቀላጠፊያ ብለው የሚሰጡት ገንዘብ የሚተዳደርበት መንገድ፣ የቤተ ክህነቱ የአገልግሎት መደቦች ስያሜና ቁጥር፣ የንዋየ ቅድሳት አስተዳደር ጥያቄ፣ የሚነሣበት እየሆነ መምጣቱን ታሳያለች ፡፡ ሙሉውን #ከመጽሔቱ ይነበብ
#ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር ደግሞ "#ጭንቀት ክፍል_፪ "በሚል ርእስ መጋቤ ሐዲስ #አእምሮ ደምሴ #የኳታር ጸርሐ አርያም ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን የብሉያትና የሐዲሳት ትርጓሜ መ/ር ደግሞ መንፈሳዊ ጭንቀት ስለሰማያዊው እና ዘለዓለማዊው ሕይወት መጨነቅና ማሰብ እንደሆነ በጥልቀት ያስተምራሉ፡፡ከመንፈሳዊ ጭንቀቶች ስቀምጣሉ፡፡ ሙሉውን ከሐመር መጽሔት ታገኛላችሁ፡፡
• #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “ከገነተ ልዑል እስከ መንበረ ልዑል”በሚል ዐቢይ ርእስ በሚል ርእስ የመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያንን ለመመሥረቱ ምክንያቶችና የአመሠራረት ሁኔታውን የሰንበትትምህርት ቤቱ አመሠራረት፣ የሊቃውንት አሻራ በመንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን ሚያዝያ 30 ቀን 2016 ዓ.ም የምረቃ መጽሔትን በምንጭነት በመጠቀም ታስቃኛለች ።
• #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ ሥር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ኦርቶዶክሳውያን ምሩቃን ለቤተ ክርስቲያን ያላቸው አስተዋፅኦ" በሚል ላለፉት ሠላሳ ዓመታት በመላው ዓለም በሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የግቢ ጉባኤያትን በመመሥረት ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ስለ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፣ ዶግማ እና ቀኖና እንዲሁም ሥርዓት እንዲያውቁ፣ ራሳቸውንም ከክፉ ነገር በመጠበቅ መንፈሳዊ ሕይወታቸውን ማነጽ እንዲችሉ አገልገሎቱን በማጠናከር ከፍተኛ ሥራ ሲሠራ መቆየቱን ያሳያል ። የግቢ ጉባኤ ተመራቂዎች ከምረቃ በኋላ በቤተ ክርስቲያን ያላቸው ድርሻ ዘርፈ ብዙ ቢሆንም ዓበይት የሆኑትን ሐመር መጽሔት ታስቃኛለች፡:
#በኪነ ጥበብ ዐምድ "#በፍላጻ የተወጋ ልብ-ክፍል ፩ "በሚል እጅብ ባሉ ሀገር በቀል የተፈጥሮ ዛፎች በተከበበ ዐፀደ ቤተክርስቲያን ውስጥ መጸለይ እጅግ ይወዳል፡፡ ከዚያ ውጣ ውጣ አያሰኘውም፡፡ አንድ ቀን እንደልማዱ ሲጸልይ ቆይቶ ጸሎቱን ሲያበቃ ከአንድ ዛፍ ሥር አረፍ አለ፡፡ እጅግ የሚያስደስት መዐዛ ቢያውደው የትመጣውን ለማወቅ ከአንገቱ ተቃንቶ ዙሪያውን ሊቃኝ ጀመረ በማለት ግሩም የኪነጥበብ ጹሑፍ ታስነብባለች ።
• #በጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምዳችን “ወርኀ ጽጌን” ክፍል አንድን በተመለከተ የሚነሡ ጥያቄዎችን መሠረት አድርገን ምላሽ ይሰጡን ዘንድ መጋቤ ሐዲስ ተስፋ ሚካኤል ታከለን በወርኃ ጥቅምት ዝግጅታችን ማቅረባችን ይታወቃል፡፡ ቀጣይና የመጨረሻውን ክፍል ደግሞ ጌታ ወደ ግብፅ የተሰደደበት ምክንያት ለምንድ ነው?

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

13 Nov, 14:40


በስደቱ ጊዜ እነ ኮቲባ ወደ ዝንጀሮና ጦጣ እንደተለወጡ ይነገራል ከሥነ ፍጥረት አንጻር ይስማማልን? የስደት ዐቢይ ምክንያቶችን እና ስደቱን ለምን በወርኀ ጥቅምት እናስባለን? ከወቅቱ ጋር የተሳሰረ ምሥጢር አለው የሚሉ ጉዳዮችን በሊቃውንት ምላሽ ይዛለች ።
ሐመር መጽሔት #፴፩ ኛ ዓመት ቁጥር ፲፩ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ !

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

10 Nov, 16:33


የማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማእከል በከተማው ከሚገኙ የመንፈሳውያን ማኅበራት ኅብረት እና ከሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር የደም ልገሳ እና የጽዳት መርሐ ግብር አከናወነ።

ኅዳር 1 ቀን 2017 ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማእከል ከመንፈሳውያን ማኅበራት ኅብረት እና ከሰ/ት/ቤት አንደንት ጋር በመተባበር በከተማዋ ሠፊ ንቅናቄ የተደረገበት የጽዳት እና የደም ልገሳ መርሐ ግብር አከናውኗል።

የአዳማ ከተማ መስተዳደር እና የከተማው  ደም ባንክ ጋር በተባባሪነት በተሳተፉበት የደም ልገሳ መርሐ ግብር ላይ አቶ በሪሶ ዶሪ የአዳማ ከተማ መስተዳድር ከንቲባ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ አቶ ሀብታሙ ግዛው የአዳማ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ም/ኃላፊ እና አቶ ኤልያስ ታደሰ የአዳማ ከተማ ጸጥታ ዘርፍ እና የሃይማኖቶች ጉዳይ ኃላፊን ጨምሮ  ከ2000 በላይ  የአዳማ ማእከል አባላት፣ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ፤የአዳማ ከተማ የሰ/ት/ቤቶች አባላት እና በአዳማ ከተማ የሚገኙ የመንፈሳውያን ማኅበራት አባላት ተገኘተው ደም ለግሰዋል።

" መልካም ሥራ ለመሥራት አንታክት" ገላ 6፥9 በሚል መሪ ቃል የተከናወነው መርሐ ግብር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና ምእመናን በአገራዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን ንቁ ተሳትፎ የሚያሳይ እንደሆነ ተጠቅሷል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

10 Nov, 07:55


https://vm.tiktok.com/ZMhbYqgEw/

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

08 Nov, 17:42


የማኅበረ ቅዱሳን ስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ሦስት አብያተ ክርስቲያናትን አስገንብቶ አስመረቀ።

ማኀበረ ቅዱሳን በአሪና ደቡብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት ጥቅምት 23፣24 እና 25  ቀን 2017 ዓ.ም  ሦስት አብያተ ክርስቲያናትን አስገንብቶ በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት አድርጓል፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት አብያተ ክርስቲያናቱን ያስገነባው ባለድርሻ እና ተባባሪ አካላትን በማስተባበር ሲሆን የሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት ሙሉ የግንባታ ወጪ 15 ሚልዮን 4 መቶ ሺህ ብር መሆኑ እና ወጪውንም በአሜሪካን ሀገር የሚገኙ የስብከተ ወንጌል ቤተሰቦች መሸፈናቸው ተገልጿል።

አብያተ ክርስቲያናቱ የተገነቡት ቀደም ባሉት ጊዜያት የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ተሰጥቷቸው አምነው ለተጠመቁ አዳዲስ አማንያን እና በቅርበት ቤተ ክርስቲያን ባለመኖሩ  ከምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን እና ሥርዓተ አምልኮ ለመካፈል ሲቸገሩ ለነበሩ ምእመናን ነው ።
የተመረቁት ሦስቱ አብያተ ክርስቲያናት የወልባክ ቅዱስ ገብርኤል ፣ የጉዶ አሸከር አቡነ ተክለ ሃይማኖት እና የተንቤል ቅዱስ መርቆርዮስ አብያተ ክርስቲያናት ናቸው።
የአብያተ ክርስቲያናቱ ቅዳሴ ቤት ተከብሮ አገልግሎት በጀመረበት ዕለት ቀደም ባሉት ጊዜያት የቅድመ ጥምቀት ትምህርት ሲሰጣቸው የነበሩ 784 አዳዲስ አማንያን ተጠምቀው የቅድስት ሥላሴ ልጅነትን አግኝተዋል ።

በምርቃት መርሐግብሩ የአሪ እና የደቡብ ኦሞ ዞኖች ሀገረ ስብከት ልዑካን ፣ የማኀበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና ሌሎች ልዑካን እና የጂንካ ማእከል አባላት እንዲሁም የጽርሐ ጽዮን የሐዋርያት አንድነት የኑሮ ማኀበር ፣ የላፎቶ ደብረ ትጉኃን ሰ/ት/ቤት እና ጥሪ የተደረገላቸው የስብከተ ወንጌል ቤተሰቦች እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

04 Nov, 10:38


የማኅበረ ቅዱሳን የሀገር ውስጥ እና የውጭ ማእከላት የጽ/ቤት ኀላፊዎች የምክክር መድረክ ተከናወነ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ማኅበረ ቅዱሳን በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በሚገኙ ማእከላቱ ውስጥ በመደበኛነት አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙ የጽ/ቤት ኀላፊዎች ጋር የውይይት እና የምክክር መርሐ ግብር ተካሂዷል።

ከጥቅምት 22 እስከ 24 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ በቆየው በዚህ መርሐ ግብር ላይ የማኅበሩን ሥልታዊ ዕቅድ ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመፈጸም በሚያስችሉ መንገዶች ላይ ሰፊ ውይይቶች እና ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል።

መርሐ ግብሩ የማኅበሩን ተቋማዊ የመፈጸም አቅም በማሳደግ እና ከባለድርሻ እና አጋር አካላት ጋር ግንኙነትን በማጠናከር ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተጠቁሟል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

03 Nov, 15:50


በማኀበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማእከል ኤስድሮስ ሥነ መለኮት ሰሚናሪ በሥነ መለኮትና ግእዝ ቋንቋ ለሦስት ዓመታት ያስተማራቸውን 33 ደቀመዛሙርት አስመረቀ፡፡

ኤስድሮስ ሴሚናሪ ጥቅምት 23 ቀን 2017 ዓ.ም በሚዙሪ ግዛት ሴንት ሉዊስ ከተማ 21 ወንዶችና 12 ሴቶችን በድምሩ 33 ደቀ መዛሙርትን ማስመረቁ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተስፋቸው መሆኗን የገለጹት ተመራቂ ደቀ መዛሙርት ወደፊትም ብዙ አገልግሎት እንደሚያበረክቱና በሰሚናሪው ቆይታቸው ያገኙት ትምህርት ለአገልግሎታቸው ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግላቸው ጠቅሰው ኤስድሮስ ሴሚናሪ ላደረገላቸውም ድጋፍ ምሥጋና አቅርበዋል።

ከምርቃት ሥነ ሥርዓቱ አስቀድሞም ለተመራቂ ደቀ መዛሙርት ተጨማሪ የሕይወትና የአገልግሎት ስንቅ የሚያገኙበት ሥልጠና መሰጠቱ ተጠቅሷል፡፡

በመርሐ ግብሩ የተገኙት የኦሃዮና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ለተመራቂዎች ዲፕሎማና የምስክር ወረቀት የሰጡ ሲሆን ማኅበረ ቅዱሳንን ከምሥረታ ጀምሮይ እንደሚያውቁትና አገልግሎቱን እንደሚደግፉ ገልጸዋል፡፡

የኤስድሮስ ሥነ መለኮት ሰሚናሪ በ2011 ዓ.ም በሰሜን አሜሪካ አህጉረ ስብከቶች እውቅና አግኝቶ ማስተማር የጀመረ ሲሆን ዘንድሮ ለሦስተኛ ጊዜ ያስመረቀ ሲሆን ሴሚናሪው በውጭ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና የውጭ ሀገር ዜጎች የግእዝ ቋንቋንና ቤተ ክርስቲያንን የበለጠ እንዲያውቋት ጠንካራ ሥራ እየሠራ እንደሆነ ተገልጿል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

27 Oct, 18:00


በማኅበረ ቅዱሳን የሰሜን አሜሪካ ማእከል የኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ 5ተኛውን ሐዊረ ሕይወት አካሄደ::

የግንኙነት ጣቢያው ጽ/ቤት እንደገለጸው መነሻውን ከኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በማድረግ ቺካጎ ወደሚገኘው የደብረ ጽዮን መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሜ ጥቅምት 16 ቀን 2017 ዓ. ም በኢንዲያና ዙሪያ የሚገኙ ከ185 በላይ ምእመናንን ያሳተፈ መንፈሳዊ ጉዞ አካሂዷል።

በዕለቱ ምክረ አበውና በርካታ መርሐ ግብራት መከናወናቸው የተገለጸ ሲሆን በተጨማሪም ክርስቲያናዊ ቤተሰብ ምን መምሰል እንዳለበት የሕይወት ልምድና ትምህርት ተሰጥቷል ተብሏል፡፡

በመርሐ ግብሩ የአሜሪካ ማእከል ሥራ አስፈጻሚ አባልና አቅም ማጎልበቻና የሰው ሀብት ዋና ክፍል ኀላፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ፍስሐ እሸቱ፣ የኢንዲያና ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ሰላም ቀሲስ ንጉሤ ገብሬ፣ ሰባኬ ወንጌል ብርሃኑ አድማስ፣ የማኅበረ ቅዱሳን ኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ አባላት እንዲሁም ምእመናን ተገኝተዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

27 Oct, 16:34


የማኅበረ ቅዱሳን ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ ለመሐል ማእከላት ሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ዋና ክፍል አባላት የልምድ ልውውጥ እና የሥልጠና መርሐ ግብር አካሄደ።

በዋና ማእከል ሕዝብ ግንኙነት እና ትብብር አገልግሎት ማስተባበሪያ የተዘጋጀው ሥልጠና ከደብረ ብርሃን፣አዳማ ፣አሰላ፣ወልቂጤ፣ወሊሶ ፣አምቦ እና አዲስ አበባ ማእከላት የተወጣጡ ከ 50 በላይ አባላት የተሳተፉበትና ለሁለት ቀናት የቆየ ሲሆን  ስለ አገልግሎት እና መሰል ጉዳዮች ውይይቶች እና የልምድ ልውውጥ ያካተተ ነበር።

ሥልጠናው ማኅበረ ቅዱሳንን እና አገልግሎቱን ከማስተዋወቅ አንጻር የሚዲያ አገልግሎት ጥቅም እና የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎት ያለው አስተዋጽኦ  ላይ ትኩረቱን ያደረገ ነበር፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

24 Oct, 13:26


ማኅበረ ቅዱሳን በ8 ማእከላት ለሚገኙ ከ1,700 በላይ ተማሪዎች የመማሪያ ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች አገልግሎት ከአንድ ቤተሰብ ለአንድ ተማሪ በሚል መሪ ቃል ፕሮጀክት ቀርጾ ወላጆቻቸውን ላጡና መማር ላልቻሉ ተማሪዎች ድጋፍ ማድረጉን ከማስተባበሪያው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት የፕሮጀክት ገቢ አሰባሰብ ባለሙያ ወይዘሮ ጣይቱ ማስረሻ እንደገለጹት በአቅም ማነስ: ሃይማኖታቸውና በማንነታቸው ምክንያት ተፈናቅለው መማር ላልቻሉ እንዲሁም በጠረፋማ አካባቢ ለሚገኙ አዲስ ተጠማቂ ተማሪዎችን ተደራሽ ያደረገ ድጋፍ ነው የተደረገው ብለዋል።

ይህ ፕሮጀክት አሁንም እንደቀጠለ መሆኑን ያነሱት የፕሮጀክት ገቢ አሰባሰብ ባለሙያዋ ወይዘሮ ጣይቱ ሁሉም ባለድርሻ አካል የበኩሉ አስተዋጽኦ እንዲያደርግ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

23 Oct, 08:12


https://www.youtube.com/watch?v=Zo1myj82qDI

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

23 Oct, 08:12


MK TV || የቅዱስ ሲኖዶስ የጥቅምት ምልዓተ ጉባኤ መከፈቱን አስመልከቶ የተሰጠ መግለጫ
https://youtu.be/di8KPxTpwSo

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

20 Oct, 07:08


https://vm.tiktok.com/ZMh5AHypy/

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

19 Oct, 13:34


የማኅበረ ቅዱሳን አዳማ ማእከል ከሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጋር በመተባበር የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ዩኒቨርስቲ ለሚገቡ ተማሪዎች የሽኝት መርሐ ግብር አከናወነ፡፡

በመርሐ ግብሩ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሲገቡ ስለሚጠበቅባቸው አካላዊ እና መንፈሳዊ ዝግጅት ሰፋ ያለ ምክር የተሰጣቸው ሲሆን 500 እና ከዚያ በላይ ውጤት ላስመዘገቡ ኦርቶዶክሳውያን ተማሪዎችም ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡

በመጨረሻም በከፍተኛ ት/ት ተቋም በሚኖራቸው ቆይታ የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንዳለባቸው እና ጎን ለጎን በግቢ ጉባኤ የሚሰጠውን መንፈሳዊ ትምህርት በመከታተል በሁለት መልኩ የተሳለ ሰይፍ መሆን እንዲችሉ የአዳራ መልዕክት ተሰጥቷቸዋል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

14 Oct, 15:13


በትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት በተለያዩ  ቋንቋዎች አገልግሎት እንዲሰጡ ለ1226 አገልጋዮች፣ ለ3650 የደረጃ 1 እና 2 ተተኪ አመራሮች ሥልጠና መስጠቱና ለ213 አገልጋዮች ወርሐዊ ደሞዝ በመክፈል ድጋፍና ክትትል ማድረጉ በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡

ስብከተ ወንጌልን ተደራሽ ለማድረግ በአማርኛና ኦሮምኛ ቋንቋዎች በርቀት ትምህርት 111 በሞጁልና 68 በኢለርኒንግ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መሠረተ እምነት ማስተማር መቻሉና ለዐይነ ሥውራን ወገኖች የውዳሴ ማርምና ሰኔ ጎለጎታ የጸሎት መጽሐፍ በብሬል ተዘጋጅቶ ተሰራጭቷል፡፡

ማኅበሩ በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ አንድነት ገዳም፣ በቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት የበደሌ ሁለገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት ግንባታ ማከናወኑ ተገልጿል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን በተጨማሪም በምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት የምስካበ ቅዱሳን ቅዱስ ዑራኤል ወሳሙኤል ዘዋልድባ ገዳም አብነት ትምህርት ቤት ግንባታ አከናውኗል፡፡

በሦስት አህጉረ ስብከት በድርቅ ለተጎዱና በሃይማኖት ተኮር ጥቃት ከስልጤ ዞን ቅበት ከተማ ተሰደው ለነበሩ ኦርቶዶክሳውያን የምግብና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በተለያዩ 7 ቋንቋዎች የተዘጋጁ 261 መዙሙራትንና በ10 ቋንቋዎች 328 መዝሙራትን የያዘ ጥራዝ ለምእመናን ተደራሽ ማድረጉ በሪፖርቱ የተገለጸ ሲሆን በማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን የተለያዩ ይዘቶችን በመጨመር የተመልካቾችን ፍላጎት ለማሳደግ የሚየስችሉ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

14 Oct, 15:13


በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ተሸለሙ።

ማኅበረ ቅዱሳን ከሰ/ት/ቤቶች ጋር በመተባበር በተለያዩ ቦታዎች ሲያስተምራቸው የነበሩ እና በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተናን ለተፈተኑ ተማሪዎች ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም የሽኝት መርሐ ግብር ተከናውኗል።

በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አዳራሽ በተከናወነው የሽኝት መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት እና የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና በ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን የወሰዱ ተማሪዎች ተገኝተዋል።

ብፁዕነታቸው በተሰጠው ሀገር አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላመጡት ተማሪ ዮናስ ንጉሠ እና ተማሪ ሄለን በርሀ የተዘጋጀውን የላፕቶፕ ኮምፒዩተር ሥጦታ ያበረከቱ ሲሆን በመርሐ ግብሩ ላይ ለተገኙት ተማሪዎችም አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

ተማሪ ዮናስ ንጉሠ ከ700 ጥያቄዎች 675 በመመለስ ከወንድ ተፈታኞች መካከል አንደኛ እንዲሁም ተማሪ ሄለን በርሀ ከ700 ጥያቄዎች 662 በመመለስ ከሴት ተፈታኞች መካከል አንደኛ መውጣታቸው ያታወቃል።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

14 Oct, 15:13


በ43ኛው አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ዋና ሥራዎች ሪፖርት ቀረበ

በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት እየተከናወነ በሚገኘው አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ላይ የማኅበረ ቅዱሳንን ሥራዎች ሪፖርት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ዋና ምክትል ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ንቡረ እድ ኤልያስ አብርሃ አቅርበዋል።

በቀረበው ሪፖርትም ማኅበሩ 310 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን በማስተማር ክህነትን እንዲቀበሉ ማድረጉ፣ ለዐይነ ስውራን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ማስተማሪያ ዐምስት የኮርስ መጻሕፍት የድምጽ ትረካ አዘጋጅቶ ማሰራጨቱ ተገልጿል፡፡

በተጨማሪም በሀገር ቤት ዐርባ ሺሕ ፣በውጭ ሀገር ደግሞ አንድ መቶ ዐስራ ሁለት አዳዲስ አማንያን የሥላሴ ልጅነት እንዲያገኙ ማድረጉ ተጠቅሷል፡፡

በከንባታ ጠንባሮ ሀላባ፣ በደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች፣ በወላይታ ሶዶ፣ በካፋ፣ በጋሞና አካባቢው ዞኖች፣ በቤንች ሸኮ፣ ሸካና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች እንዲሆም በዳውሮ አህጉረ ስብከት በካህናት እጥረት ተዘግተው የነበሩ 34 አብያተ ክርስቲያናት ካህናት ተቀጥሮላቸው አገልግሎት እንዲጀምሩ ተደርጓል ተብሏል፡፡

በደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች፣በወላይታ ሶዶ፣ በቤንች ሸኮ፣ ሸካና ምዕራብ ኦሞ ዞኖች አህጉረ ስብከት ለአዳዲስ አማንያን መገልገያ የሚውሉ ዐምስት ሕንጻ አብያተ ክርስቲያናትና ዐራት መካነ ስብከት አዳራሾችን አሠርቶ ለአገልግሎት ማዋሉ በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡

በ169 የአብነት ትምህርት ቤቶች ለሚገኙ 224 መምህራንና 2018 ደቀ መዛሙርት የገንዘብ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን 73 ተማሪዎችን የአባ ጊዮርጊስ ነጻ የትምህርት እድል ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ተብሏል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

14 Oct, 15:13


43ኛው አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የመጀመሪያ ቀን የከሰዓት በኋላ ውሎ ተጀመሯል።

በአሁኑ ሰዓት የተለያዩ አህጉረ ስብከቶች የ2016 ዓ.ም የአገልግሎት አፈጻጸም ሪፖርቶችን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።

ማኅበረ ቅዱሳን ( Mahibere Kidusan)

14 Oct, 15:13


“አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው”ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ገለጹ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት 43ኛው ዓለም አቀፍ መደበኛ ጉባኤ መክፈቻ ላይ ለተገኙ ተሳታፊዎች መልእክት አስተላልፈዋል።

ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው አሁን ባለን የአስተዳደር ክፍተቶችና በውስጣችን ያሉ ግልጽነት የጎደላቸው አሠራሮች ለአገልግሎታችን እንቅፋት እየሆኑብን ነው። በዚህ ጉባኤ በቤተ ክርስቲያናችን የሚታየውን  ችግር ለመፍታት በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ማምጣት ይገባል ሲሉ አፅዕኖት ሰጥተዋል፡፡

ቅዱስነታቸው ጨምረው እንደገለጹት ቅዱስ ሲኖዶስ ተግባራዊ እንዲሆን የወሰነውን የቤተ ክርስቲያን የ10 ዓመት መሪ ዕቅድ ውጤታማ ለማድረግ ሁላችንም በትብብር መሥራት ይገባናል ብለዋል።

በዛሬው ዕለት የተጀመረው 43ኛው አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ ከሀገር ውስጥ እና ውጪ ከሚገኙ አህጉረ ስብከቶች፣ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አድባራት እና ገዳማት እንዲሁም ከተለያዩ መንፈሳዊ ማኅበራት የተወከሉ ተሳታፊዎች በተገኙበት እየተከናወነ ይገኛል።

26,398

subscribers

4,078

photos

45

videos