Hilina Belete @hilinabelete Channel on Telegram

Hilina Belete

@hilinabelete


Deacon Hilina Belete is a servant of the Ethiopian Orthodox Tewahido Church.

Hilina Belete Telegram Channel (English)

Welcome to the Hilina Belete Telegram Channel, where you can stay connected with Deacon Hilina Belete, a devoted servant of the Ethiopian Orthodox Tewahido Church. In this channel, you will find inspirational messages, prayers, and teachings from Deacon Hilina Belete to help you strengthen your faith and spirituality. Whether you are a member of the Ethiopian Orthodox Church or simply seeking spiritual guidance, this channel is a valuable resource for anyone looking to deepen their connection to God. Join us in this journey of faith and enlightenment with Deacon Hilina Belete on Telegram today!

Hilina Belete

10 Feb, 11:25


አንድ ሰሙን "ደከመኝ" ማለትን ሳበዛ በወዳጆቼ በኩል ተግሣፅና ምክር ያጣድፈኝ ጀመር። "አንተኮ ለራስህ በቂ ጊዜ ስለማትሰጥ ነው፤ እስኪ ጥቂት ዐረፍ በል" ፣ "እስኪ ሙሉ የጤና ምርመራ አድርግ" እና የመሳሰሉት ተግሣፃዊ ምክሮች በዙብኝ። እኔ ቸል ስል አንዳንድ የልብ ወዳጆች "እ...ምን አደረግህ?" እያሉ አማራጭ አሳጡኝ። እኔም ባየኋቸው ቁጥር ከምሸማቀቅ ብዬ ወደ ሆስፒታል ሄጄ ሙሉ የጤና ምርመራ አደረግሁ።

በጤናው ዘርፍ ረዘም ላለ ጊዜ ስሠራ አንዳንድ በጣም የተጨነቁ ታካሚዎች የምርመራ ውጤታቸው ምን እንደ ሆነ ሲጠይቁኝና ውጤታቸውም normal ሲሆን ከጭንቀታቸው እንዲላቀቁና ዘና እንዲሉ "ጤና በዝቶቦታል" እላቸዋለሁ። የእኔ ምርመራም አብዛኛውና ዋና ዋናው ጉዳይ እንዲያ የሚያስብል ነበር። ግን... አንድ ሕመም አለብህ ተባልኩ። ደነገጥሁ።

ከፊት ለፊቴ ተቀምጣ ከምታወራኝ ሐኪም ጋር እያወራሁ ሁለት ነገሮችን በጥልቀትና በመረበሽ አስብ ጀመር። የመጀመሪያው ሞት ነበር። በዚህ ጥልቀት ስለ ሞት አስቤ አላውቅም። ለካስ እሞታለሁ! ይህን እውነት ባውቅም በዚያች ቅጽበት እንደ ተሰማኝ ሆኖ አስቤው አላውቅም። ታሞ የማያውቅ ሰው ሆኜ ለትንሿ ነገር ደነበርሁ። የሐኪሟ አነጋገር እኔ ካለሁበት ሁኔታ አንጻር እንክብካቤን የተሞላ እንዳልሆነ በራሴ ሚዛን መዝኜ አዘንሁባት። ታዘብኳት!
ደግሞ ሌላ ትዝብት... ለካስ በሐኪም ቤት ውስጥ ሰው ታሞ ሲመጣ ከዚህ ዓይነት ስሜት ጋር ነው። ለእኛ ሆስፒታሉ የሥራ ቦታችን ነው። የምንውልበትም እንደ ሥራ ቦታችን ነው። ለታካሚው ግን ጤናውን የሚሻበት፣ የሚታከምበት፣ የሚፈወስበትም ነው። የታመመ ሰው ለካ የሚያክመውን ሐኪም፣ የጤና ባለሙያን ብቻ ሳይሆን ከሜዲካል ሳይንሱ በላይም የሚያጽናናውን ወዳጅም ይፈልጋል። ለካስ የጤና ባለሙያ የሚዳብስ ወዳጅም መሆን ይገባዋል። እንዲህማ ከሆነ ለንስሐ አባቴ የምነግረው ገና ብዙ በደል አለብኝ። ይህ ሙያ ለእኔ ከባድ በመሆኑም ብዙ እንደማልገፋበትም ማሰብ ጀመርኩ።

ደግሞ እንደ ገና ራሴን ታዘብኩ። ድንጋጤዬን "ሞት ወደ ላይኛው ዓለም የምንሻገርበት ድልድይ ነው" ብዬ በተደጋጋሚ ከመስበኬ ጋር አነጻጽሬ ራሴን ታዘብኩ። "አበው ራሳቸውን የሚጎሽሙበት በሽታን እንዲሰጣቸው ይጸልያሉ፤ ፈጣሪ ጤናን ብቻ ሳይሆን በሽታንም በመስጠት ይጎበኛል" ብዬም አስተምሬ ነበር ለካ! እንዲህ መርበድበዴን አንድ ከሥሬ የተማረ ምእመን ቢያይ ምን ይል ይሆን? እኔን ብሎ መምህር! (በርግጥ እንዲህ ብለው ሲጠሩኝ ሁሌም ይከብደኛል)። ለካስ ሲናገሩትና ሲኖሩት አንድ አይደለም። (ታሞ የማያውቅ ሰው ችግር ነው፤ ለሚያልፍ ነገር እንዲህ መረበሽ። እግዚኦ!)

ወደ አእምሮዬ የመጣው ሌላኛው አሳብ ደግሞ "የጀመርኳቸውን እነዚያን ሁሉ ሥራዎች ማን ሊጨርሳቸው ነው? ሞት ሊቀድመኝ?" አልኩ። በቅድሚያ ያሰብኩት መጽሐፎቼን ነው። የመጨረሻ መጽሐፌ አውግስጢኖስ ከታተመ 6 ዓመት ሊሞላው ነው። ከዓመታት በፊት የተጀመሩ የተወሰኑ ወጥና የትርጉም ሥራዎች ነበሩ። አንዳንዶቹ ለመገባደድ ከጫፍ ደርሰው የተተዉ፣ አንዳንዶቹ የተጋመሱ፣ አንዳንዶቹ የተጀመሩ፣ የተቀሩት ደግሞ ቅድመ ዝግጅታቸው ተጠናቆ መጻፍ ብቻ የሚቀራቸው ነበሩ።

(ምናልባት ይህች አጋጣሚ እነዚህ የዘነጋኋቸውን ሥራዎች እንዳስታውስ መልአኩን ልኮ ጎኔን የጎሸመባት ትሆናለች)

የዘኆኅተ ብርሃን ሚዲያን ስናስጀምር በሥሩ ያሉትን አገልጋዮች ሁልጊዜም "እንደሚሞት ሰው ሥሩ" እላቸው ነበር። እኔም በዚህች ቀን ሞቱ እንደ ተቆረጠለት ሰው መፍጠን እንዳለብኝ ማሰብ ጀመርኩ። ከሥራና ከሌሎች አገልግሎቶች (በተለይም ከዘኆኅተ ብርሃን ሚዲያ) በሚተርፈኝ ጊዜ እነዚህ ሥራዎች ላይ አተኮርኩ።

(በነገራችን ላይ የሕመሙን ጉዳይ ለመንደርደሪያነት አነሣሁ እንጂ አሁን ጤና በጤና ነኝ - ለነገሩ ያኔም ሕመም አለብህ አሉኝ እንጂ እኔ አልታመምሁም ነበርኮ)

ያሰብኳቸውን ወጥ ሥራዎች ከመሥራቴ በፊት እጄ ላይ ያሉት ጅምሮች ማለቅ እንዳለባቸው ተሰማኝ። በቅድሚያ የተመለስኩበት ሥራ መምህር ገብረ እግዚአብሔር ኪደን የመሰሉ ወዳጆች "ከምን ደረሰ?" እያሉ ዘወትር ከሚያስታውሱት ሥራ ነው። የሴባስቲያን ብሮክ - የቅዱስ ኤፍሬም - Luminous Eye - ብርህት ዓይን።

፩- ብርህት ዓይን

ይህችን የትርጉም ሥራ ያጋመስሁት የዛሬ 5 ዓመት ነበር። ሕንዳዊው የቲዎሎጂ የዶግማ መምህራችን ፋዘር ጆሲ ጄኮብ ይህን መጽሐፍ እንተረጉም ዘንድ ደራሲው መፍቀዱን ከነገረኝ በኋላ ዘግይቼ ብጀምረውም ካጋመስኩት ኋላ ግን ትቼው ነበር። የቅዱሱ ሊቅ ወዳጆችና ሥራው መጀመሩን የሚያውቁት ጥቂቶች "ከምን ደረሰ" ሲሉኝ እያፈርኩ መለስ እልበትና መልሼ እተወው ነበር። ይኸው አሁን እርሱ ፈቅዶ ከእጄ ሊወጣ ነው መሰል!

ዛሬ - የካቲት 3 የቅዱስ ኤፍሬም በዓል ነው። በዚህች ዕለት መጽሐፏ ኅትመቷን ጨርሳ ከእጃችሁ ባትገባም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በዐቢይ ጾም ውስጥ እንድትደርስ የሚቻለንን እያደረግን ነው። ስለ መጽሐፉ በበቂ ሁኔታ ስለ ተነገረ ብዙ አልልበትም። ብቻ ሴባስቲያን ብሮክ ለቅዱስ ኤፍሬም እንዳደረገው ቅዱስ ያሬድና አባ ጊዮርጊስም እንዲህ ዓይነቱን ሥራ የሚሠራላቸውን "አንድ ሴባስትያን ብሮክን ቢያስነሣላቸው" ብዬ የምመኝበት ዓይነት ግሩም ሥራ ነው።

ጥቂት እርማት ተደርጎባትና ሴባስትያን ብሮክን የማናገር ሥራችንን እንደ ጨረስን ወደ ኅትመት ትገባለች።

፪- ወደ ሙስሊሞች የተላኩ መልእክታት

ይህኛውም እግዚአብሔር ከረዳኝ ከዐቢይ ጾም አይዘልም። ወደ መገባደዱ ነው። በውስጡ ሁለት መልእክታትና አንድ ደግሞ የታሪክ ማስረጃዎች (historical apologetics) ስብስብን የያዘ ነው። ይህም ተጋምሶ ለዓመታት ቢቆይም በመጨረሻ የኅትመት ፀሐይን ሊያይ የቀረበ ነው። ያድርሰን!

፫- ሦስተኛው የሦስት ሰዎችን ታሪክ የያዘ ነው። የአንዱን ብቻ ለመናገር ያህል ይህችን ልበል:- በግርድፉ የዛሬ ስድስት ወይም ሰባት ዓመት አካባቢ አለርት ሆስፒታል ውስጥ እየሠራሁ አንድ አባት ቢሮዬ ድረስ መጡ። ብሩክ ሰለሞን ይባላሉ (በነገራችን ላይ አሁን ያሉበትን ለሚጠቁመኝና ለሚያገናኘኝ ምስጋናዬ ከልብ ነው)። የሚኖሩት በስዊዘርላንድ ሲሆን ለአጭር ጊዜ ዕረፍት ሲመጡ ፈልገው እንዳገኙኝ ነገሩኝ። ያን ጊዜ አጫጭር ጽሑፎችን አዘውትሬ እየጻፍኩ የተለያዩ የቫይበር ግሩፖች ላይ ለጥፍ ነበር። እነዚያን ጽሑፎች እርሳቸው እየወሰዱ በስዊዘርላንድና በተለያዩ የአውሮፓ ሀገሮች ውስጥ ላሉ ግሩፖች ይልኩ እንደ ነበርና በዚያ እንደሚያውቁኝ ነገሩኝ።
ማርቲን ፍላድ የተባሉ ለ60 ዓመታት በኢትዮጵያ የኖሩ አንድ ሰው ነበሩ። በፈረንሳይኛ የተጻፈ የኢትዮጵያ ቆይታቸውን የተመለከተ ግለ ታሪካቸውን ወደ አማርኛ እንድመልሰው ፈልገው ነበር። ግለ-ታሪኩ ያልታተመና ተጽፎ በረቂቅነት የተቀመጠ ነበር። ፈረንሳይኛን ከሰላምታና ከትውውቅ በሚያሻግር ሁኔታ እንደማልችል ብነግራቸውም ኃላፊነቱን ወስጄና በተለያዩ አካላት ታግዤ ራሴ እንድሠራው ተማጸኑኝ። በጎዶሎ ልቤ ተማጽኗቸውን ተቀበልኩ።

(በነገራችን ላይ የማርቲን ፍላድ ታሪክ ከጊዜያት በኋላ ወደ እንግሊዝኛ ተመልሶ በአማዞን የግብይት መድረክ ላይ አይቼዋለሁ። ዋጋው ግን አይቀመስም፤ ከ1ሺህ ዶላር ያልፋል።)

Hilina Belete

10 Feb, 11:25


ከብዙ መዘግየት በኋላ ወደ ሥራው ስገባ እግረ መንገዴንም የሌሎች የተወሰኑ ሰዎች ግለ-ታሪኮችን ወደ ማየት ገባሁ። የተወሰኑትን ሠርቼ ባሳትማቸው ጠቃሚ ይሆናሉ ብዬ ጀምሬ ሳልገፋበት ቀረሁ። ሆኖም ከዚያች ከሳምንታት በፊት ከተጎሸምሁባት ቀን ጀምሮ መለስ ብዬ ካየኋቸው ሥራዎች መካከል እነዚህ ግለ ታሪኮች ይገለጻሉ።
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ከዐቢይ ጾም በኋላ የሚፈጸምና ከእጃችሁ የሚገባ ስለ ሆነ ለጊዜው ሸፈን አድርገነዋል። ያድርሰን!

(ማስታወሻ:- አሁናዊው የኅትመት ወጪና መጓተቱ ካቀድኳቸው ጊዜዎች ሊያዘገየኝ እንደሚችል ታሳቢ ይደረግልኝ)

ለማንኛውም ዛሬ እነዚህን ጉዳዮች መግለጽ ያስፈለገኝ በብዙ የተራዳኝ የቅዱስ ኤፍሬም ዓመታዊ በዓሉ ስለ ሆነ ነው። ዳግመኛም የመጀመሪያው መጽሐፍ በቀጥታ እርሱን የሚመለከት በመሆኑም ነው።

ከበዓሉ ረድዔት በረከትን ይክፈለን። ምልጃው አይለየን!

“ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን...
በገዛ እጄ የተጻፈ የእኔ ... ሰላምታ ይህ ነው፤ የመልእክቴ ሁሉ ማስረጃ ይህ ነው፤ እንዲህ እጽፋለሁ"
(ያዕ.4÷15፣ 2ተሰ.3÷17)

ዲ/ን ሕሊና በለጠ ዘኆኅተ ብርሃን

Hilina Belete

08 Feb, 21:56


“ጌታ ቢፈቅድ ብንኖርም ይህን ወይም ያን እናደርጋለን...
በገዛ እጄ የተጻፈ የእኔ ... ሰላምታ ይህ ነው፤ የመልእክቴ ሁሉ ማስረጃ ይህ ነው፤ እንዲህ እጽፋለሁ"
(ያዕ.4÷15፣ 2ተሰ.3÷17)

Hilina Belete

25 Jan, 20:20


ይህችን ትምህርትም ተጋበዙልኝ!

https://youtu.be/ab-GsKxsUqM?si=fQbSARndX-3ix03i

Hilina Belete

24 Jan, 19:17


https://youtu.be/J5op8-AuC3I?si=cw0RNA0aKTUw_azC

Hilina Belete

12 Jan, 11:49


"ወደ ጌታ እቅፍ ዘንበል ያለው ሐዋርያ"

ወደ ጌታ እቅፍ ዘንበል ያለው ሐዋርያ ዮሐንስ መሆኑን በመጽሐፉ የገለጸው አውሳብዮስ የተባለው የታሪክ ጸሐፊ ነው።
ወደ ጌታ እቅፍ ዘንበል ማለት ግን እንዴት ይሆን? የጌታ እቅፍ ሙቀቱ እንደ ምን ይሆን? ይህን ሊመልስ የሚችለው እቅፉን የሚያውቀው ሐዋርያውና እመቤታችን ይመስሉኛል።

ገነት፣ መንግሥተ ሰማያትን በአብርሃም እቅፍ እንመስላታለን - በሞተ ሥጋ የተለየንን "ነፍሱን በአብርሃም እቅፍ ያሳርፍልን" እንድንል። ዮሐንስ ግን ወደ ጌታ እቅፍ ዘንበል አለ። የአብርሃም እቅፍ ገነትን ከመሰለ፣ ዮሐንስ ያረፈበት የጌታ እቅፍ እንዴት ያለ ይሆን?

ሲከፋንና የሚጎረብጥ ስሜት ውስጥ ስንሆን እቅፋቸውን የምንመኘው ሰዎች አሉ። ሽጉጥ ብለንባቸው ብንደበቅ የምንመርጣቸው። በእቅፋቸው ውስጥ ሆነን ብናነባ የምንፈልጋቸው። ከፍቅራችን ጽናት የተነሣ ከእቅፋቸው መለየት የማንፈልግ ሰዎች ይኖሩናል።

ዮሐንስ ግን መጽናናትን ፈልጎ ይሆን? ወይስ ከፍቶት? የጌታው እቅፍ ውስጥ የሸጎጠው ምን ይሆን? በርግጥ ቁጹረ ገጽ ነውና ይህ ቢያስኬድም፣ ያኔ የጌታ መከራ ገና በመሆኑ: ወደ ጌታው እቅፍ ዘንበል ያደረገው ፍቁረ እግዚእነቱ ነው እንላለን። የፍቅሩ ጽናት ከእቅፉ ከተተው። ያ የጌታችን እቅፍ ግን ምን ያህል ያጽናና!? ምን ያህል ያስደስት!?

ሕፃን ልጅን እናትና አባቱ "ትወደኛለህ?" ቢሉት "አዎ" ይላቸዋል። "እንዴት አድርገህ?" ቢሉት የመውደዱን መጠን የሚገልጸው በቻለው ኃይሉ ሁሉ ዕቅፍ በማድረግ ነው። ያለ የሌለ ኃይሉን ተጠቅሞ በዕቅፉ ለማስጨነቅ ይሞክራል። እመቤታችን ጌታን በልጅነቱ ስታጫውተው መውደዱን እንዴት ገልጾላት ይሆን? እንዴትስ አቅፏት ይሆን? አምላክ እናቱን ሲያቅፍስ እንዴት ይሆን? እርሷስ ዕለት ዕለት አቅፋ ስታሳድገው አምላክን በእናትነት ማቀፍ እንደ ምን ይሆን?

ስምዖን አረጋዊ ጌታን ለቅጽበት ቢያቅፈው ከዚያ በኋላ መሞትን ተመኘ። ጌታን ማቀፍ ማዳኑን እንደ መቅመስ መሆኑን ነገረን። ከእናቱ እቅፍ ተቀብሎ አቀፈውና "...እግዚአብሔርንም እየባረከ እንዲህ አለ፦ 'ጌታ ሆይ፥ አሁን እንደ ቃልህ ባሪያህን በሰላም ታሰናብተዋለህ፤ ዓይኖቼ በሰዎች ሁሉ ፊት ያዘጋጀኸውን ማዳንህን አይተዋልና"። (ሉቃስ 2:28-31)። (ልጅን ከእናቱ እቅፍ ሲያወጡት እንዲያለቅስ፣ ስምዖን ከእናቱ እቅፍ ሲወስደው ሕፃኑ ጌታ አይኑን ወደ እናቱ እያንከራተተ አልቅሶ ይሆን?)

ስምዖን አንድ ጊዜ አቅፎትና አይቶት ከዚህ ምድር መለየትን ከለመነ፣ ዕለት ዕለት አቅፋ ዓይን ዓይኑን የምታየው እመቤታችን ገናናነቷ ምን ይረቅ!? ምን ይደንቅ!?

ኧረ በጌታ የታቀፈ የዚህ ሐዋርያ እቅፍ፣ ጌታ ሲያቅፋት ያደገች፣ እርሷም ስታቅፍ ያሳደገችው የድንግል እቅፍ ምን ይመስል ይሆን!?

ቅዱስ ያሬድን አብልጠው የሚወዱት አንድ ሊቅ "እኔ ስሞት እንዲያው ቢፈቅድልኝ በአብርሃም እቅፍ ሳይሆን በቅዱስ ያሬድ እቅፍ ብሆን" ብለው ተመኙ። አንባቢ ሆይ! ማድላት እንዳይመስልህ፤ ዘይቤ ነው።
እኔ ደግሞ ዛሬ ይህን ሳሰላስል የዮሐንስንና የድንግልን እቅፍ ተመኘሁ።

እንኳን ለውዱ ሐዋርያ በዓል አደረሰን!

(በድጋሚ የተለጠፈ)

ዲያቆን ሕሊና በለጠ ዘኆኅተብርሃን

Hilina Belete

20 Nov, 06:08


ኅዳር 15 በዓሉ ነው። እስኪ ታሪኩን፣ ገድሉን በጥቂቱ ያድምጡ።

https://youtu.be/UY64Oe5BPLY?si=NfPJAe_X0orhJLrZ

Hilina Belete

12 Nov, 18:33


መቅደስ ወደ መቅደስ ውስጥ የገባችበት ዕለት ምን ይደንቅ?
ማኅደረ መለኮት ወደ ማኅደረ መለኮት ውስጥ የገባችበት ዕለት ምን ይረቅ?
ኆኅተ ብርሃን ወደ ኆኅተ ብርሃን ውስጥ የገባችበት ዕለት!
ለዛሬ ወር ያድርሰን!
(ፎቶ:- ኤረር በዓታ ገዳም)

Hilina Belete

02 Nov, 06:21


አበባ፣ ፍሬውና ምሳሌነታቸው

https://youtu.be/ebJAfnRkKjA?si=8kqApNCfZrWA6WFk

Hilina Belete

18 Oct, 05:27


የማትረግፍ አበባ የማትጠወልግ
ዘውትር 'ምታብብ
መዓዛ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ናት
መድኃኒተ ሕዝብ
...
የሲና ሐመልማል እሳት የተስማማት
መቃጠልን 'ማታውቅ የመለኮት ሌማት
የእርሷ ድንግልና ዘላለማዊ ነው
የማትረግፍ ሲላት ያሬድን አየነው
...
ተቀጥፋ የቆየች የአቤሜሌክ ቅጠል
66 ዓመት ደርቃ ሳትቃጠል
መስጠት ያላቆመች የልምላሜዋን ጠል
ፍሬዋ ክርስቶስ አበባ ናት ድንግል
...
ከአሮን በትር ላይ አብባ የተገኘች
የደረቀን ዓለም ማለምለም ታውቃለች
አባ ጊዮርጊስም አላት ፈርከሊሳ
እንደ አንበሳ ኃጢአቱን ድል እንድትነሳ
...
የምታሳሳ እናት ውብ ናት እንደ አበባ
በምልጃዋ ያመነ ስንቱ ገነት ገባ
አባ ጽጌ ድንግል ማበቧን ያወቀው
ማኅሌቷን ታጥቆ ተመስጦ ነጠቀው
...
በጽጌ ማኅሌት ንዒ ንዒ እያልን
እኛም ከሊቁ ጋር ልንጠራት ሌት አለን
አበባ ነፍሳችን ጠውልጋ እንዳትረግፍ
የምልጃዋ ጥላ በእኛ ላይ ይረፍ።

ዜማ:- ቀሲስ ግርማ አዳነ
ግጥም:- ዲ/ን ሕሊና በለጠ ዘኆኅተብርሃን

https://youtu.be/pPA--15XgA4?si=ohvj079wDCoxpjCE

Hilina Belete

14 Oct, 08:51


ኦርቶዶክሳውያን ሴቶች ሲሣሉ ጸጉራቸው ይሸፈናል። የማርያም እንተ ዕፍረት ግን ይገለጣል።
በማርያም እንተ ዕፍረት፣ በማርያም እኅተ አልአዛርና በማርያም መግደላዊት መካከል ልዩነታቸው እንዲህ ተብራርቷል።
ሦስቱም ሽቱ የያዙበት ጊዜ አለ። ሁለቱ ቀብተዋል። አንዷ አልቀባችም። ሁለቱ እንተ ዕፍረት ይባላሉ።

ሊቀ ሊቃውንት ሥሙርን በዘኆኅተ ብርሃን በኩል ያድምጡና ያትርፉ።

https://youtu.be/gBmf1opk8A4?si=zHpjadVTyVp3zlhw

Hilina Belete

12 Oct, 20:33


በልቅሶና በጩኸት የወርቅና የብር መፈተን የሆነ መፈተንሽ እንደ ምን ያለ ፍጹም ድንቅ ነገር ነው? ... የፈጣሪ የኢየሱስ እናት ሆይ! ቀን በፀሐይ ሐሩር፣ ሌሊትም ፍጹም ምሳሌ በሌለው ውርጭ ልምላሜያዊ ሰውነትሽ እንደ ምን ጠወለገ?... 'ከመ ዘእሳት ዘሐቅል ሕሊናየ ውእየ' ... እመቤቴ ማርያም ሆይ! ሀገርን የሚጠብቁ ሰዎች 'የእኔንና የተወደደ ልጄን ልብስ ገፈፉ' በማለት በተናገርሽው ነገርሽ ሕሊናዬ እንደ በረሓ እሳት ተቃጠለ..... እንደ ውኃ ፈሰስሁ፤ ዐጥንቴ ሁሉም ተበተነ፤ ኃይሌም እንደ ገል ልምላሜን ዐጥቶ ደረቀ፤ ምላሴም በጉረሮዬ ውስጥ ዱረቀ"
(አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)

Hilina Belete

05 Oct, 13:29


- ኢየሱስ በዚህ ይሸፈናልን?
- ምንኩስና ስንፍና ነውን?
- ኦርቶዶክስን የመዝለፍ ልምምድ
- የኑሮ መቃወስ
- ክርስቲያናዊ መፍትሔው ምንድን ነው?

https://youtu.be/_jQWWGPBl7I?si=LvhvJwvN-kaw9L_P

Hilina Belete

30 Sep, 09:42


ውድ የእመቤታችን ወዳጆች!
እንኳን ለብዙኃን ማርያም በዓል አደረሳችሁ!
የማርያም ወዳጅ የሚለውን ይህን ትምህርት ተጋበዙልኝ!

https://youtu.be/L0skZvJ1_w4?si=9JnpmdmHzhMgZg29

Hilina Belete

27 Sep, 17:21


"ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ትእምርተ መስቀል የከበረ ነው።
እግዚአብሔር ምሳሌው የሆነ ትእምርተ መስቀል ከሁሉ አስቀድሞ ተፈጠረ። በሱ አምሳል አዳምን ፈጠረው።
ለመላእክትም የመስቀል ምልክት አክሊል አላቸው። እንደ መብረቅ ያለ ዘውድም አላቸው። የመስቀል አምሳል በትርም አላቸው። ፊታቸውንም በመስቀል ምልክት ይሸፍናሉ። የመስቀል ማዕዘን አራት እንደ ሆነ የመንበሩም ጎኖቹ አራት ናቸው።
ይህ መስቀል የሄኖስ የሽቱ እንጨቱ ነው። የአብርሃም የወይራ እንጨቱ፣ የይስሐቅ የነጭ ሐረጉ፣ የያዕቆብ የዕጣኑ እንጨት ነው።
ይህ መስቀል የሙሴ የሃይማኖት በትሩ ነው። ይህ መስቀል ክንድን በኤፍሬምና በምናሴ ራስ ላይ በማስተላለፍ የጥላ ምልክት ነው።
ይህ መስቀል የኤርምያስ የሎሚ በትሩ ነው። የኢሳይያስ የስሙ መታሰቢያ ነው።
ይህ መስቀል በሰሎሞን ያለ የእንኮይ እንጨት ነው። ከእንኮይ አነሳሁህ፤ በዚያም የወለደች እናትህ ታመመች ብላ ይህች ሙሽራ ስለ ሙሽራዋ ብዙ ተናግራለችና። ስለ መስቀሉም ከጥላው በታች መቀመጥን ወደድሁ አለች...."
ድርሳነ መድኃኔ ዓለም ዘቀዳሚት

እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በዓል አደረሳችሁ!

Hilina Belete

21 Sep, 06:36


የስኬት ሕይወት

https://youtu.be/AJdcoh7ykKk?si=8SN2P4yu7fl7Cnpm

Hilina Belete

11 Sep, 16:26


በጾም የተጀመረ ነገር ፍጻሜው መልካም ነው። ጌታችን የ3 ዓመት ከ3 ወር አገልግሎቱን የጀመረው በጾም ነው። ሐዋርያት የተልእኮአቸው ጅማሬ በጾም የተባረከ ነበር። በጥንት ዘመን ባለ ትዳሮች የትዳር ዘመናቸውን የሚጀምሩት በጾም ነበር። ተክሊል ፈጽመው 40 ቀናትን ይጾሙና ሰርግን ያደርጋሉ። አበው የተጋድሎ ዘመናቸው የሚጀመረውም የሚፈጸመውም በጾም ነው። እኛም አዲሱን ዓመት በጾም ጀምረናል። እግዚአብሔር የባረከው የሰላምና የበረከት ዘመን ያድርግልን!

እንኳን ለዘመነ ማቴዎስ አደረሳችሁ!

ዲ/ን ሕሊና በለጠ

Hilina Belete

07 Aug, 19:14


እንኳን ለጾመ ፍልሠታ አደረሳችሁ!
ይህችን ተጋበዙልኝ!

https://youtu.be/pkSgA0pDmU8?si=vYXES45Xo-S5Vwi_

Hilina Belete

22 Jul, 16:16


ይህች እጅ ውዳሴ ማርያምን የጻፈች እጅ ናት። የቅዱስ ኤፍሬም ቀኝ እጅ ናት። ከ13ቱ የግሪክ ክልሎች መካከል አንዱ በሆነው በመካከለኛው መቄዶንያ ውስጥ በሚገኘውና "የገነት አንድ ማዕዘን (ጥግ)" ተብሎ በሚታወቀው የቅዱስ ኤፍሬም ገዳም ውስጥ ትገኛለች። በገዳሙ ዋናው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይህች ቅድስት እጅ ከቅዱስ ኤፍሬም የግድግዳ ላይ ሥዕል (fresco) እና ከእመቤታችን ሥዕል ጋር በአንድነት ትገኛለች። በረከቱ ይደርብን! ለመሳለም ያብቃን!

Hilina Belete

22 Jul, 08:34


ሐምሌ 15 የቅዱስ ኤፍሬም በዓሉም አይደል?
እስኪ ይህችን የሕይወት ታሪኩን ከዘኆኅተ ብርሃን ሚዲያ ላይ ተጋበዙልኝ!
https://youtu.be/30odpzraaF4?si=zyzydc2dvSzFDLjC

Hilina Belete

21 Jul, 20:38


ቅዱስ ኤፍሬም ጥበብን ያስተምረው ዘንድ እግዚአብሔርን ለመነ። በደረሰበት ቦታም አንዲት ሴት ትኩር ብላ አየችው። እርሱም "ምነው?" አላት። እርሷም "እኔስ አንተን ማየቴ አያስገርምም፤ ከወንድ ተፈጥሬአለሁና። አንተ ግን የተፈጠርክበትን አፈር ትተህ እኔን ማየትህ ይገርማል" አለችው። ቅዱስ ኤፍሬምም ጥበብን ከማይጠብቅበት ሥፍራ በማግኘቱ እግዚአብሔርን እያመሰገነ ሔደ።

እንኳን ለቅዱስ ኤፍሬም በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ!

Hilina Belete

14 Jul, 10:43


ፈቃደ እግዚአብሔር

https://youtu.be/FdtM5zw5TzQ?si=MPqE2e2U9ZQIuBPf

Hilina Belete

06 Jul, 12:13


ቡና መጠጣት ኃጢአት ነውን?
ንስሐ ገብቶ ራስን ማጥፋትስ?
መሳቅ መጫወትስ?
https://youtu.be/a9YMNaAr5Os?si=0pz8mls6lUWa7RVW

Hilina Belete

02 Jul, 18:07


እንደ ካህን ልጆቿን ያጠመቀችው ቅድስት ሣራ እነኋት - 4 ደቂቃ በማትሞላ ትረካ ተዋወቋት።

https://youtu.be/alp7AIl7bC4?si=CXWRpU8xH4W8gONr

Hilina Belete

26 Jun, 17:27


ከዘፋኝነት የተመለሰው ሰማዕት

https://youtu.be/mve8E_Ev7Ig?si=U5daOy6j3_u8n9Ru

Hilina Belete

21 Jun, 19:34


ጰራቅሊጦስ
Subscribe በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ!

https://youtu.be/sW9CgYnNGCo?si=yUYYt95arRFqIEjh

4,886

subscribers

303

photos

14

videos