Ethiopian Sugar Industry Group @etsugar Channel on Telegram

Ethiopian Sugar Industry Group

@etsugar


የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ

Ethiopian Sugar Industry Group (Amharic)

የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ተጠቃሚ የሆነው ETSugar ለእርስዎ ያዳምጡ!
እባኮትን በዚህ ቦታ በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሚገኙ ጂኦፖችን እና በፈሳሽ ሌሎች በመጠቀም ከእኛ ጋር እርምጃለን። ETSugar በዓለም ዙር ሁኔታን እንዴት ማሰልመያ እንደምንችል እዚህ ይገልጻል።nnአሁንም ምሳሌን ቢኖር በሚቀጥለው ETSugar መንካተኛ ችሎት እና ማስፈጸም ለመስራት ዜና እና ቅርብ ጉዳይን መማከሚያ በሚለዎት ተጠቃሚ የሆነው እ.ቤት ብመልክተኞች ሁሉም ምንም ይልቃል ። ETSugar ከሩቅ በኋላ የሆነው ጊዜ ሊበልጥ ትልቅ ነው ።nnየቴሌግራም ቴክኖሎጂያችንን ገልጸዋል እናምናለን ግን የእርስዎ ህጎችን ምንጭ አንድን ዕቅድ እያሳተፉ እና በሌሎች ነቀሮች ሰላም ለማነውር ማስፈጸም እንዲረዳ ይህን እንዲሻል እንዲሁም ፓይልን እንዲጠቁ ከእኛ ጋር ለማንኛውም አገልግሎት ፣ ድርጊያ እና እንዲሁም መንካታቸውን ለማፍረስ ስለ ጀምሩት እስከዚያ ገንዘብ ድረስ በተዘጋጅም ሰፋ ወዳልአዳንቀባላቸው ።

Ethiopian Sugar Industry Group

31 Dec, 10:34


በኩር ጣእም /ዘጋቢ ፊልም / Etv |https://www.youtube.com/watch?v=kT9LmSfBgxo

Ethiopian Sugar Industry Group

27 Dec, 13:00


በኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3/1 ስኳር ፋብሪካ ዋና ከተማ የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ቦኖዎች ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3/1 ስኳር ፋብሪካ ዋና ከተማ የነበረውን የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ችግር ለመቅረፍ የተገነቡ አምስት የመጠጥ ውሃ ቦኖዎች ለአገልግሎት ክፍት ሆኑ፡፡
የመጠጥ ውሃ ቦኖዎቹ ታህሳስ 18 ቀን 2017ዓ.ም በፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈይሳ ፈቃዱ ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት መደረጋቸውን የፋብሪካው የሕዝብ ግንኙነትና ተሳትፎ የሥራ ክፍል ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል፡፡
ቦኖዎቹ ለአገልግሎት ክፍት ሲደረጉ ንግግር ያደረጉት የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈይሳ ፈቃዱ የውሃ መስመሩ ለአገልግሎት መብቃቱ ቀደም ሲል የነበረውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ይመልሳል ብለዋል፡፡
የመጠጥ ውሃውን ቤት ለቤት ለማዳረስ የመስመር ዝርጋታ ሥራ በተያዘው በጀት ዓመት በራስ አቅም እንደሚከናወን የፋብሪካው የፕሮጀክት፣ መስኖና ሲቪል ሥራዎች ክትትል መምሪያ ሥራ አስኪያጅ አቶ አብዮት ኤና በበኩላቸው ገልጸዋል፡፡
ለጉድጓድ ቁፋሮ፣ በሰከንድ 8 ሊትር በሚገፋ ፓምፕ ከጉድጓድ የወጣው ውሃ ለሚጠራቀምበት ማጠራቀሚያ ግንባታና ከማጠራቀሚያ ወደ ቦኖዎቹ ለማገናኘት እንዲሁም ለፓይፕ ዝርጋታ፣ ለመንገድ ማቋረጫ ስትራክቸሮች ግንባታ፣ ለጄኔሬተር ቤት እንዲሁም ለቦኖ ግንባታ ስራ በአጠቃላይ ከ157 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጓል፡፡
ባይጌት ኮንስትራክሽን፣ ደቡብ ውሃ ሥራዎች እንዲሁም ንዑድ ኮንስትራክሽን የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ በተለያዩ ሥራዎች መሳተፋቸው ተመልክቷል፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

25 Dec, 11:09


ስኳር ፋብሪካዎች ከክረምት ጥገና በኃላ መደበኛ
ስኳር የማምረት ሥራቸውን ጀምረዋል

Ethiopian Sugar Industry Group

25 Dec, 08:01


ስኳር ፋብሪካዎች ከክረምት ጥገና በኃላ መደበኛ
ስኳር የማምረት ሥራቸውን ጀምረዋል
_________________________________
ከ2016 ዓ.ም የክረምት ወራት መግባት ጋር ተያይዞ አጠቃላይ የጥገና ሥራ ሲያከናውኑ የቆዩት ስኳር ፋብሪካዎች መደበኛ የማምረት ሥራቸውን ጀምረዋል፡፡
የፋብሪካዎቻቸውን የተለያዩ ማሽነሪዎችን፣ የእርሻና የመስኖ ማሽነሪዎች እንዲሁም የመስኖ አውታር አጠቃላይ የጥገና ሥራዎችን በክረምቱ ወራት አከናውነው ስኳር ማምረት የጀመሩት ስኳር ፋብሪካዎች ወንጂ ሸዋ፣ መተሐራ፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3/1 እና ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 ስኳር ፋብሪካዎች ሲሆኑ የፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካም የክረምት ወራት አጠቃላይ የጥገና ሥራውን አጠናቆ ወደ ኦፕሬሽን እየገባ ነው፡፡
ወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ የክረምት ጥገና ሥራውን አጠናቆ ምርት ማምረት ከጀመረ አንድ ወር ያለፈው ሲሆን ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ከሶስት ሳምንት፣ ኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 እና መተሐራ ስኳር ፋብሪካ ከሁለት ሳምንት በፊት የክረምት ጥገና ሥራቸውን አጠናቀው ወደ ምርት ገብተዋል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ የፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ሰሞኑን የክረምት ጥገና ስራውን አገባዶ ወደማምረት ስራ እየገባ ይገኛል፡፡
በእስከአሁኑ ሂደት ፋብሪካዎቹ ከ300ሺ ኩንታል የሚበልጥ ምርት ማምረት ችለዋል፡፡ በዚህም ወንጂ ስኳር ፋብሪካ በቀን እስከ 7ሺ ኩንታል ስኳር ማምረት ወደቻለበት ውጤታማ የአፈጻጸም ደረጃ መድረስ የቻለ ሲሆን ሌሎቹም በተመሳሳይ ሁኔታ በቀን አሁን ከደረሱበት ማለትም በቀን በአማካይ 3ሺ ኩንታል ከፍ እያሉ እንደሚሔዱ ይጠበቃል፡፡ የጉልበት ሰራተኞች አቅርቦት ችግር በአሁኑ ወቅት ፋብሪካዎቹን እያጋጠማቸው ያለ ጎላ ያለ ችግር መሆኑን ማየት የተቻለ ሲሆን የሰው ሐይል ከሚገኝባቸው ክልልች ጋር ተቀርርቦ በመስራት ችግሩን ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አመቻቺነት መንግስት በበጀት ዓመቱ ለስኳር ፋብሪካዎች የውጭ አገር መለዋወጫ ግዢ የሚውል 27 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር መድቦ ከዚህ ውስጥ እስካሁን 10 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚደርስ የመለዋወጫ ግዢ ተከናውኗል፡፡
እንደሚታወቀው ስኳር ፋብሪካዎች በክረምት ወራት በጭቃ ምክንያ ሸንኮራ አገዳ ከማሳ አውጥተው መደበኛ የስኳር ምርት የማምረት ሥራ ለማከናወን አዳጋች ስለሚሆንባቸው እንዲሁም የፋብሪካዎችም የተለያዩ ማሽነሪዎች በመደበኛ የምርት ወቅት ለሰባትና ስምንት ወራት ሃያ አራት ሰዓት በስራ ላይ ስለሚሆኑ ወደ አዲስ የምርት ዘመን ሽግግር ከመደረጉ አስቀድሞ የፋብሪካዎች አጠቃላይ የጥገና ሥራ በክረምት ወራት ማከናወን መደበኛ የስኳር ኢንዱስትሪ የአሰራር ባህል ሆኖ የሚታወቅ ነው፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

17 Dec, 08:36


የሀዘን መግለጫ
----------
በአገራችን የስኳር ልማት ዘርፍ የጎላ ሚና የነበራቸው፣ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ካጠናቀቁ ማግስት ጀምሮ የስኳር ኢንዱስትሪውን በመቀላቀል በተለያዩ ከፍተኛ የኃላፊነት ቦታዎች ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ሲተጉ የነበሩትና በምክትል ዋና ዳይሬክተርነት ደረጃ የቀድሞው ስኳር ኮርፖሬሽን የፋብሪካ ግንባታና ኦፕሬሽን ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት አቶ ደረጀ ጉተማ በድንገተኛ ህመም ከዚህ አለም በመለየታቸው የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል፡፡

አቶ ደረጃ ጉተማ የከፍተኛ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ በስኳር ምርምርና ስልጠና ዘርፍ በመመደብ፣ በፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ ከተለያዩ የሥራ ኃላፊቶች እስከ ዋና ሥራ አስኪያጅነት ድረስ በማገልገል ከፍተኛ ልምድ ያካበቱ እንዲሁም የቀድሞው ስኳር ኮርፖሬሽን ሲቋቋም እና አዳዲስ ስኳር ልማት ፕሮጀክቶች ሲስፋፉ የካበተ ሙያቸውን በማበርከት አይነተኛ ሚና የተጫወቱ የሀገሪቷ የስኳር ልማት ዘርፍ ዋልታ ነበሩ፡፡

አቶ ደረጀ ጉተማ በተግባር የተፈተሸ ልምዳቸውንና የዘርፉ ዕውቀታቸውን በመጠቀም "የስኳር ነገር - የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ከየት ወዴት እንዴት" በተሰኘ ርዕስ በዘርፉ መጽሐፍ የጻፉ በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ታሪክ ብቸኛው ሰው የነበሩ ሲሆኑ እስከ ህልፈተ ህይወታቸው ድረስም የፊንጫኣ ስኳር ፋብሪካ እና የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሥራ አመራር ቦርድ አባል ሆነው ሲያገለግሉ ነበር፡፡
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በአቶ ደረጀ ጉተማ ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጹ ለቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለስኳር ኢንዱስትሪ ዘርፍ የሙያ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን ይመኛሉ፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

16 Dec, 06:37


የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ የበጀት ዓመቱን
የስኳር ምርት ሥራ ጀመረ
____________________________
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ የ2017ዓ.ም የስኳር ምርት ሥራውን በመጀመር ከ ታህሳስ 5 ቀን 2017ዓ.ም ጀምሮ ስኳር በማውጣት ላይ ይገኛል፡፡
የፋብሪካው የክረምት ጥገና ከተጠናቀቀ በኋላ ዋና ሥራ አስኪያጁ አቶ ፈይሳ ፍቃዱ፣ ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችና ሰራተኞች በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት አገዳ የመፍጨት ሥራውን እንደጀመረም ተመላክቷል፡፡
በኦሞ ኩራዝ ስኳር ልማት ፕሮጀክት የሚገኙት የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 2 እና 3 ስኳር ፋብሪካዎች በአካባቢው ካለው የአየር ንብረት ጋር በተያያዘ የማምረቻ ጊዜያቸው በዓመት ሁለት ጊዜ መሆኑ ይታወሳል፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

20 Nov, 11:40


የፋብሪካ ውጤታማነትን በቀጣይነት ለማሳደግ በባለቤትነት ስሜት ኃላፊነትንና ድርሻን መወጣት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ
______________________________

የአመራር እና የስራ አፈጻጸም ችግሮችን ለይቶ የመፍታት አቅማችንን የበለጠ በማጎልበት የኦሞ ፋብሪካዎችን ውጤታማነት ለማሳደግ የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወዮ ሮባ አስታወቁ፡፡
ዋና ስራ አስፈጻሚው ከሐምሌ 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው የአቅም ግንባታ እና የስራ አፈጻጸም ማሻሻያ ግምገማዊ ስልጠና በዋናው መስሪያ ቤት እና በፋብሪካዎች ጭምር በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን በማስታወስ በወቅቱ አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም ግምገማ ማካሄድ አስፈላጊ መሆኑን ያመላከቱ ሁኔታዎች ነበሩ ብለዋል፡፡

በዚሁ መሰረት በኦሞ 2 እና በኦሞ 3 ስኳር ፋብሪካዎች የእያንዳንዱን ሰው ሚናና አስተዋጽኦ መለየት በሚያስችል ሁኔታ ዝርዝር ግምገማ ሲደረግ መቆየቱን ተናግረዋል፡፡ በተለይ የኦሞ 3/1 ስኳር ፋብሪካ ከሚገኝበት መልክዓ ምድራዊ ስፋት እና ከያዘው የሰው ኃይል እንዲሁም ከአገዳ ማሳ ስፋት አንጻር በልዩ ትኩረት የግምገማ ስራው እንዲካሄድ ተወስኖ የዋና መስሪያ ቤት የስራ ኃላፊዎች ጭምር በተሳተፉበት ሁኔታ ላለፉት ሶስት ሳምንታት ሰፊ እና ዝርዝር ግምገማ ሲካሄድ መቆየቱን አመልክተዋል፡፡
ቅዳሜ ህዳር 07 ቀን 2017ዓ.ም. በኦሞ 3/1 ስኳር ፋብሪካ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከቀትር በፊት ከስራ መሪዎች ጋር ከቀትር በኋላ ደግሞ ከሰራተኞች ጋር የማጠቃለያ የውይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት የቀረበው የማጠቃለያ ሪፖርት እንዳመለከተው አብዛኛው ሰራተኛ የተቋሙን ችግር ለመቅረፍ የበኩሉን ጥረት እያደረገ እንደሚገኝ ለመረዳት ቢቻልም፤ ውስን የፋብሪካው ኃላፊዎችና ሰራተኞች ዝርፊያ፣ የጸጥታ ማደፍረስ፣ ስራ ማደናቀፍና ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት አለአግባብ መንቀሳቀስን ጨምሮ ከባድ የዲሲፒሊን ጥሰት ላይ ተሳትፈው ተገኝተዋል፡፡

እንዲህ ያለው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ከስራ መሪዎችና ሰራተኞች የማይጠበቅ ከመሆኑም በላይ የፋብሪካውን የስራ አፈጻጸም የመጉዳት ትልቅ አቅም እንዳለውም ሊታይ እንደሚገባ ዋና ስራ አስፈጻሚው አመልክተዋል፡፡

በስራ አመራር፣ ስራ አፈጻጸምና በባለቤትነት ስሜት ኃላፊነትን መወጣት ላይ ትኩረት አድርጎ በተካሄደው በዚህ ግምገማ አንዱ ለስኬት ሌላው ደግሞ ለውድቀት አልሞ ይንቀሳቀስ እንደነበር ከሪፖርቱ መረዳት መቻሉን አቶ ወዮ አመልክተው በዚህ ሁኔታ እድገትም ሆነ ውጤታማነትን ማሰብ ፈጽሞ እንደማይቻል ጠቁመዋል፡፡ ከዚህ ይልቅ የአላማ አንድነትንና የባለቤትነት ስሜት ፈጥሮ ወደፊት መራመድ ላይ አተኩሮ መስራት ለሁሉም የሚጠቅምና ከሁሉም የሚጠበቅ እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡

በዚሁ የግምገማው ውጤት መሰረት ተገቢው የማስተካከያ እርምጃ እንደሚወሰድ የጠቆሙት የግሩፑ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፋብሪካው ወደኦፕሬሽን ስራ ለመግባት ጥቂት ቀናት ብቻ የቀሩት እንደመሆኑ የማስተካከያ እርምጃው ፈጥኖ እንደሚተገበር አረጋግጠው በሂደቱ ፋብሪካውን ውጤታማ ለማድረግ ተቋማዊ ውግንና ይዘው አጥፊዎችን ለይተው ለማውጣት በንቃት የተሳተፉትን እንዲሁም ሂደቱን በማስተባበር ለተሳተፉት ሁሉ ዋና ስራ አስፈጻሚው ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በማጠቃለያ መድረክ ላይ የተሳተፉ ኃላፊዎችና ሰራተኞች ከአቅም ግንባታው ስልጠና ጀምሮ እስከ ዝርዝር ግምገማ የዘለቀው የፋብሪካውን ተልእኮ ከማሳካት አኳያ የእያንዳንዱ ኃላፊና ባለሙያ ሚናን አስተዋጽኦ ለመለየት የተሰራው ስራ በቀጣይ የፋብሪካውን ውጤታማነት እያሻሻሉ ለመሄድ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ተናግረዋል፡፡

የኦሞ ፋብሪካዎች እ.ኤ.አ. ከታህሣሥ የመጀመሪያ ሳምንት ጀምሮ ስኳር ወደማምረት ስራ እንደሚገቡ ይጠበቃል፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

19 Nov, 14:11


የግሩፑ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "የህልም ጉልበት ለዕምርታዊ ዕድገት" በሚል ርዕስ ውይይት አካሄዱ
__________________________

ለኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "የህልም ጉልበት ለዕምርታዊ ዕድገት" በሚል ርዕስ ለፌዴራል የመንግስት ተቋማት ሠራተኞች በተዘጋጀ ሰነድ ላይ ማክሰኞ ህዳር 10 ቀን 2017ዓ.ም በአዲስ አበባ ፍትሕ ቢሮ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡
ውይይቱን የመሩትና የተዘጋጀውን ሰነድ ያቀረቡት በግሩፑ የማርኬቲንግ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታፈሰ አሰፋ ባደረጉት ገለጻ፤ ውይይቱ ወቅታዊ፣ የመንግሥት ሠራተኛው መንግስት ምን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ግንዛቤ የሚያገኝበት፣ በቀጣይ ምን እንደሚጠበቅበት የሚገነዘብበትና መንግሥት ከሠራተኛውና ህዝብ ምን እንደሚጠብቅ የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡
ለውይይቱ የቀረበው ሰነድ ከሰባ ዓመታት ጀምሮ የነበሩ ሀገራዊ የፖሊቲካ ሁኔታዎች እና እነዚህን ሁኔታዎች ተከትሎ የመጣው ለውጥ፣ ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ቀንድና ከአፍሪካ አንጻር ያላትን የኢኮኖሚና የዲፖሎማሲያዊ ተጽዕኖና ቀጣይ ተስፋ፣ ያላት የመልማት አቅም ምን እንደሚመስል በዝርዝር ቀርቧል፡፡
የብልጽግና ፓርቲ አመሠራረት፣ ፓርቲው አሁን የሚገኝበት ሁኔታ በዚህ ውስጥ ለፓርቲው መመስረት አስፈላጊ የሆኑ ምክንያቶችንም ዘርዝረዋል፡፡
አክለውም የብልጽግና ፓርቲ ትሩፋቶችና ተግዳሮቶች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ምን ምን እንደሆኑ በስፋት አንስተዋል፡፡
በተጨማሪም ተቀባይነት ያለው ሀገረ መንግሥት ግንባታ እና ስለወል ትርክት ምንነት፣ የወል ትርክት ግንባታና አስፈላጊነትን በተመለከተ፣ ባለፉት የለውጥ ዓመታት ስለተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ዘርዝረዋል፡፡
በማጠቃለያቸውም ሠራተኛው ለግልና የጋራ ህልሞች መሳካት መሰናክሎችንና ጎታች ግፊቶችን የሚሻገር፣ ከፍ ያለ ትጋትና ቁርጠኝነት እንዲሁም የአገልጋይነት መንፈስ መላበስ እንደሚጠበቅበት አሳስበዋል፡፡
ከብልሹ አሠራር የጸዳ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዩን እርካታ ማረጋገጥ የመንግስት ሠራተኛው ቁልፍ ኃላፊነት መሆኑንም አቶ ታፈሰ አስገንዝበዋል፡፡
ሰነዱ ከቀረበ በኋላ ከውይይቱ ተሳታፊዎች ለቀረቡ ጥያቄዎች ያቀረቡ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

11 Nov, 08:18


በስኳር ፋብሪካዎች በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች የክልሉን ወጣቶች ተጠቃሚ ማድረግ የሚያስችል ውይይት ተካሄደ
_________________________________________________
https://etsugar.com/esig/am/2024/11/11/በስኳር-ፋብሪካዎች-በሚፈጠሩ-የሥራ-ዕድሎ/

Ethiopian Sugar Industry Group

01 Nov, 07:14


In case you missed it

Ethiopian Sugar Industry Group

31 Oct, 06:57


በኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ተቀጥረው ከሚሰሩየሱርማ ማሕበረሰብ አባላት ጋር ውይይት ተካሄደ
___________________
በኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ በኦሞ ኩራዝ ቁጥር 3 ስኳር ፋብሪካ ተቀጥረው በመስራት ላይ ከሚገኙ የሱርማ ማሕበረሰብ አባላት ጋር ጥቅምት 19 ቀን 2017ዓ.ም የአካባቢውን ጸጥታና ደህንነት በተመለከተ ውይይት ተካሂዷል፡፡

በውይይቱ ላይ የኦሞ ኩራዝ ቁጥር 1/3 ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ካሳ ተስፋዬ፣ የአገር መከላከያ ሠራዊት እና ፌደራል ፖሊስ አመራር አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
በውይይቱ ወቅት የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ ባደረጉት ንግግር ፋብሪካው የሚያከናውነውን የልማት ሥራ በአግባቡ ማከናወን እንዲቻል የአካባቢ ጸጥታና ደህንነትን በማረጋገጥ ረገድ የማህበረሰቡ ሚና የላቀ ነው ብለዋል፡፡

በፋብሪካው ተቀጥረው በመስራት ላይ የሚገኙ የማህበረሰቡ አባላት ለፋብሪካው ሠላምና ጸጥታ መጠበቅ የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ ፋብሪካው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግ ኢንጂነር ካሳ ጠቁመው በአርብቶ አደሩ ስም የሚነግዱ ወንጀለኞችን ማጋለጥና ለሕግ አሳልፎ መስጠት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡

በውይይቱ የተሳተፉ የፋብሪካው ሠራተኛ የሆኑ የማህበረሰቡ አባላት በበኩላቸው የአካባቢው ደህንነትና ጸጥታ እንዲጠበቅ የመረጃ ልውውጣቸውን በማጠናከር እና ወንጀለኞችን አጋልጦ በመስጠት ከፋብሪካው ጋር በጋራ እንዲሚሰሩ መግለጻቸውን የፋብሪካው የሕዝብ ግንኙነትና ተሳትፎ ክፍል ያደረሰን ዘገባ ያመለክታል፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

30 Oct, 13:09


በ2017 የመጀመሪያ 100 ቀናት የመንግስት ዕቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት ተካሄደ
___________________
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በያዝነው በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የመንግስት የዕቅድ አፈጻጸም ላይ ጥቅምት 20 ቀን 2017ዓ.ም በኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርትና ሎጁስቲክስ አገልግሎት ድርጅት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት አድርገዋል፡፡
በውይይቱ የተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ 100 ቀናት የመንግስትን የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት የግሩፑ የማርኬቲንግ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ታፈሰ አሰፋ እንደ አገር የተካሄዱ የሪፎርም ሥራዎች ያስገኟቸውን ውጤቶችና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ምን እንደሚመስሉ በወቅቱ ዘርዝረዋል፡፡

በገለጻቸውም ዓለም ዓቀፍ የፖለቲካና የኢኮኖሚ አዝማሚያዎች ምን እንደሚመስሉ፣ የሚጠበቁ ሁኔታዎች ምን እንደሆኑ፣ አገሪቱ ያደረገችው የኢኮኖሚ ሪፎርም አፈጻጸም ምን እንደሚመስል እንዲሁም የስኳር ልማት ዘርፉን ጨምሮ እንደ አገር የዋና ዋና ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ አስረድተው በስብሰባው ተሳታፊዎች በኩል ሰፊ ውይይት ተደርጎበታል፡፡
አገሪቱ በልዩ ልዩ የምጣኔ ሀብት መለኪያዎች መልካም ውጤቶችን ማስመዝገቧን የተናገሩት ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው የግሩፑ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በአገር ደረጃ የተመዘገበው ውጤት ቀጣይ እንዲሆን በተሰማሩበት የስኳር ልማት ዘርፍ የበኩላቸውን መወጣት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል፡፡

Ethiopian Sugar Industry Group

28 Oct, 09:02


የሐዘን መግለጫ
በወንጂ ሸዋ ስኳር ፋብሪካ በፋብሪካ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጂነት፣ በፋብሪካ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጂነት እንዲሁም በቀድሞው ስኳር ኮርፖሬሽን የፋብሪካ ግንባታ ኮንትራት አስተዳደር ሥራ አስፈጻሚነት በአጠቃላይ በዘርፉ ከ20 ዓመታት በላይ ባገለገሉት በአቶ ፈቃደ ስሜ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ኃዘን እየገለጽን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መጽናናትን እንመኛለን፡፡
የኢትዮጵያ ስኳር ኢንዱስትሪ ግሩፕ