አባወራ @abawera Channel on Telegram

አባወራ

@abawera


አባወራ፦አባትነት፣ ባልነት፣ ወንድነት፣ ራስነት
+251-9-11-67-46-87

አባወራ (Amharic)

አባወራ ምን ነው? ለምሳሌ፡ አባወራ በአማርኛ ለሚቀጥሉ ሁኔታዎችን እና ህብረት በፊት ሌሎችን ፍላጎትን ከአፍሪቃሚ እንዲሾም ማስተርጉን ይችላሉ። ማንኛውም ባህርይ እንኳን ኢትዮጵያዊያኖቹ በአፍሪቃሚን ለመሾም ያግዛሉ። ከዚህ በታች ይመልከቱ እስከማንኛውም ባህር በመርበት በዚህ አፍሪቃሚ መልኩ ከሚቀጠረው የብፁዕ ሴቶችና ልጆች ጋር ይገኛሉ። ይህ ምሳሌ ሌላ ምንጭ ቅንያትን በሙስና ለመነውርና ወንድም ሲባከክን በማክሰክ ለያዘንም ይፈልጋል። ስለአባወራ ይህን ይካሄዳሉ፡ +251-9-11-67-46-87

አባወራ

18 Feb, 18:11


https://youtu.be/oqYiJ5K1Onc?si=97bi-22TkeY2hnyM

አባወራ

18 Feb, 06:26


ከሥራችን ይልቅ ስማችን ያስጨንቀናል!
========================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ከሥራችን ይልቅ የሁልጊዜ የሚያስጨንቅ ራስምታታችን ብልሹ ምግባራችን ሳይኾን እርሱን ጠቅሰው ሰዎች የሰጡን ስም ነው።

"እንዲህ አትበለኝ፣ እንዲያ አይደለሁም፣ እንደዚህ ነኝ እንዴ እኔ፣ ሁለተኛ እንዲህ እንዳትለኝ፣ እንዲያ ነህ እንዲህ ነህ ይሉኛል..." ስንል ያስጨነቀን የተሰጠን ስም ይምሰል እንጂ ስሙ የገለጠው ምግባር እንዳለብን ፍንጭ ይሰጣል።

ብዙውን ጊዜ ወድቀን የተገኘንበት የተነቀፍንበትም ምግባር ሳይኾን የተጠራንበት ስም ይረብሸናል። በዚያም ራሳችንን ለመከላከል እንጋጋጣለን እንጂ የተነቀፈ ሥራችንን ለማረም አንሞክርም!

ይህ ክፉ ዐመል ከተራው ማኅበረሰብ ይልቅ፤ እውነትና ጽድቅን በማስተማር በተግባርም በመኖር ሊቀድሙ ከሚገባቸው ልሂቃን ዘንድ የተለመደ እንዳውም የባሰ ነው።

እውነት እየተገፋች፣ እየተደፋችና እየተቀበረች በመጣችባት ዐለም እውነትን ሊያስተምሩ በእውነት ሊኖሩና ለትውልዱ ምሳሌ ሊኾኑ የሚገባቸው ሊቃውንት ነበሩ።

እነርሱ ግን ሰውነትን፣ አንድም ሕሊናን ከምታጠራው እውነት፤ እንዲሁም ሰው የሚድንበትን እውነት ከመግለጥ ይልቅ በአስመሳይነት የቆሸሸ ምግባራቸው እንዳይገለጥ ስማቸው ያስጨንቃቸዋል እንጂ።

ከዚህም ብሶ "እንዴት እንወቀሳለን፣ እንዴት ሊቁን ትወቅሳለሁ፣ እንዴት የቀለም ቀንዱን ትነካለህ፣ እንዴት..." ይሏችኋል፤ እነዚያው በእነዚህ "ሊቃውንት" የሚሸነገሉ ምስኪኖች።

ከዚህም የተነሳ ስለ እውነት፣ ጽድቅና ፍትሕ ሊጮሁ የሚገባቸው እነዚያ ኢፍትሐዊነት በትውልዱ ላይ ነግሦ ቢያዩም፣ ግፍ ተለምዶ ሕዝቡ ቢሰቃይም፣ በደል ኃጢያትም ሠልጥኖበት ሰውነቱን ቢያጣም ጉዳያቸው አይኾንም።

ዘወትር አሳሳቢው ጉዳይ "የማይዳሰስ፣ የማይወቀስ፣ የማይከሰስ"፣ የሚበሉበት፣ የሚከብሩበት፣ የሚሾሙበት፣ የሚሸለሙበት ስማቸው ክብራቸው እንጂ ነው። ተከታዮቻቸውንም እንዲሁ አስተምረዋቸውልና አሳልፈው ለሚሰጧቸው ስለእነርሱ ይሞቱሏቸዋል።

ወንድምዓለም! "እንዲህ ነህ" ሲሉህ ትበሳጫለህን? እንዲያ ያለህንስ "ካልገደልኩ" ትላለህን? ምናልባት ይህ ራስክን እንድታይ ጥሩ እድል አድርገህ ብትጠቀምበትስ?

ከውጪ ወዳንተ ከተወረወረው፣ ከተለጠፈብህም ስም ይልቅ ከሰው ደብቀህ፣ ከእይታ አርቀህ፣ ከእውቅና ሰውረህ የምትሠራው፣ ምናልባትም ልክ እንዳልኾነ ሕሊናህ የሚያውቀው የሚነግርህም እርሱ አንተን በተለይም ነፍስህን እንዲያቆሽሽ ተገንዘብ!

ስም የሰው ልጅ አንድን ነገር፦ ሰውም ቢኾን እንሰሳ ወይንም እቃ ለመሰየም ሲጠቀምበት፤ ከሞላ ጎደል አካሉን ዐይቶ፣ ግብሩን ተከትሎ፣ ጠባይ ባሕሪውን ተረድቶ የሚሰጠው ነው።

ስለኾነም የተጠራህበት ስምህ "አይመጥነኝም፣ አይገልጠኝም" ከማለት ይልቅ፤ ራስክን ታዘብ!ካልወደድከው፦ መለወጥ የሚችል አቋም ቁመትክን፣ አስተሳስብና ድርጊትክን አሻሽለው፣ ከነውርም አንጻው።

አባወራ

18 Feb, 04:38


https://youtu.be/LeGqWKAUKHg?si=9SyDze1S8pdXzUNm

አባወራ

17 Feb, 07:06


https://youtu.be/7-RrqMz9klg?si=8vzLLP--o-my_zNx


ትውልድን አጥፊ ማርክሳዊ አጀንዳ በቤተክርስትያን

አባወራ

17 Feb, 04:03


ከድርጊቱ ይልቅ ስሙ የሚያስጨንቀን እኛ
=========================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ሙሰኝነቱ ሳይኾን ሙሰኛ መባሉ
ሆዳደርነቱ ሳይኾን ሆዳደር መባሉ
አመጸኝነቱ ሳይኾን አመጸኛ መባሉ
ዘማዊነቱ ሳይኾን ዘማዊ መባሉ
ባንዳነቱ ሳይኾን ባንዳ መባሉ
ባለጌነቱ ሳይኾን ባለጌ መባሉ
ነውረኝነቱ ሳይኾን ነውረኛ መባሉ
ሌብነቱ ሳይኾን ሌባ መባሉ
ሴሰኝነቱ ሳይኾን ሴሰኛ መባሉ
ሱሰኝነቱ ሳይኾን ሱሰኛ መባሉ
አመንዝራነቱ ሳይኾን አመንዝራ መባሉ
ስንፍናው ሳይኾን ሰነፍ መባሉ
ሰበበኛነቱ ሳይኾን ሰበበኛ መባሉ
ደካማነቱ ሳይኾን ደካማ መባሉ
ፈሪነቱ ሳይኾን ፈሪ መባሉ
ዋሾነቱ ሳይኾን ዋሾ መባሉ
አታላይነቱ ሳይኾን አታላይ መባሉ
አስመሳይነቱ ሳይኾን አስመሳይ መባሉ
አንባገነንነቱ ሳይኾን አንባገነን መባሉ
ከዳተኛነቱ ሳይኾን ከሐዲ መባሉ
አለሌነቱ ሳይኾን አለሌ መባሉ
ስግብግብነቱ ሳይኾን ሆዳም መባሉ
ጎስቋላነቱ ሳይኾን ጎስቋላ መባሉ
ሆደባሻነቱ ሳይኾን ሆደባሻ መባሉ
ብሶተኛነቱን ሳይኾን ብሶተኛ መባሉ
አላዝኝነቱ ሳይኾን አላዛኝ መባሉ
ጅላጅልነቱ ሳይኾን ጅላጅል መባሉ
አጭበርባሪነቱ ሳይኾን አጭበርባሪ መባሉ
ዝርክርክነቱ ሳይኾን ዝርክርክ መባሉ
.
.
.
አልጫነቱ ሳይኾን አልጫ መባሉ

ለምን ይኾን ከድርጊታችን ይልቅ የምንለይበት የድርጊቱ መጠሪያ ስሙ የሚያስጨንቀን? መቼስ ይኾን ስሙን የምንጠላውን ያክል ድርጊቱን የምንጠላው?

ድርጊቱን የእኛ አይደለምን? እኛ የሠራነው በተግባር የተገለጥንበትስ አይደለምን? የምንጠላው ከኾነስ ለመተው አንሞክርምን?

ደግሞስ ድርጊቱ ከእኛ ዘንድ ልማድ ኾኖ ካለ ለምን ሰዎችን እንዲህ ብላችሁ አትጥሩን እንላለን? "አይደለንም፣ አልሠራንም" ብለን ልንክድ ነውን?

በየትኛውስ የፍርድ አደባባይ(በሰማዩ ወይንስ በምድሩ) በሠራነው ሥራ፣ በድርጊቱም ሳይኾን ሰው እኛን በጠራበት ስሙ እጠየቃለን?

በእንዲህ ያለ "ስሜቴን አትንኩብኝ፣ ስሜቴን ጠብቁልኝስ" ትውልድ ይታነጻልን፣ ሰው ይድናልን፣ ሰውነቱን ያገኛታልን፣ ነፍሱንስ ያተርፋታልን?

ክፉ ሥራቸውን፣ መጥፎ ምግባራቸውን በአደባባይ የምናውቅላቸው ሰዎች በዚያ ሊጠሩ፣ ሊነቀፉ፣ ሊወቀሱና እንዲታረሙ ግድ ሊባሉ አይገባምን?

አለበለዚያ ግን ይህንን ክፉ፣ መጥፎ ወይንም ደካማ ማንነታቸውን ልጆቻችንም ኾኑ ታናናሾቻቸው የእነርሱን ፈለግ የሚከተሉ አይደለምን?

ይህስ ክፉ ሥራ፣ መጥፎ አመል፣ ደካማ ጎን ነገ እንድ ጽድቅ መሥሪያ መሣሪያ ተደርጎ አይታይምን?

ወንድምዓለም! አሁን ሴትን ያማከለ ኾኖ እየመጣ ባለው ቤተሰብና ማኅበረሰብ "የትውልዱን ስሜት ጠብቁ፣ ክፉ ሥራ አይታችሁ ለመጥራት ለመውቀስም አትቸኩሉ፣ ትውልዱ ስስ ደካማ ተሰባሪ ነው" ይሉናል።

ይህ ግን ትውልዱን በተለይም ወንዱን ወደ ተፈጠረለት ልዕልና፣ ወደ ተጠራለት ዓላማ ያደርሰዋልን ወይንስ ያንኑ "ደካማና ተሰባሪ" ማንነቱን እያስታመመ የሚያላዝን አልቃሻ ያደርገዋል?

አንተ ይህንን የምታነበው፦ ሴሰኛ ከኾንክ "ሴሰኛ" ስትባል አትበሳጭ። "ሴሰኛ" መባልህ ካበሳጨህ ሴሰኝነትክን ተው! እርሷም አመንዝራ ከኾነች(ከባሏ ሌላ እየሃደች የምትተኛ ከኾነ) "አመንዝራ" ስትባል አይክፋት፤ ሌሎችም "እንዲህ አትበሏት ስሜቷ ይጎዳል" አይበሉ!

ታናሼ! ራስክን ታዘብ! ስንት ሰው የማያውቀው፣ ባለማወቁም የማንጠራበት ክፉ፣ መጥፎ፣ ተልካሻ ሥራ አለን። እነርሱን ሰው ስላላወቀብንና እንዲያም ስላልተጠራንባቸው "የእኛ አይደሉም" ብለን ልንጽናና ነውን?

ከድርጊታችን ይልቅ በሠራነው ሥራ መጠራታችን ሲኾን ለጸጸት፣ ለንስሃ፣ ለይቅርታ፣ ለእርቅ፣ ለንጽሕና፣ ለልዕልና፣ ለልሕቀትስ እንደንቆርጥ (ለቁርጥ ሕሊና) የሚያነቃን አይኾንምን?

ወንድምዓለም! በተጠራህበት ስም ራስክን ኾነህ ካገኘኸው እና እንዲያ ያስጠራህን ያንንም ድርጊት ሠርተኸው ከተገኘህ? "እንዲህ አትበሉኝ!" ብሎ መቆጣት መበሳጨቱም ምንም ጥቅም የለውም ብቻ ሳይኾን ጉዳቱም የበዛ ነው!

ይልቁንስ ስሙ ሲጠራ የጠላኸውን ያንን ተግባር ሲያስታውሱህ፣ ነቅሰው ሲጠቁሙህ ከመበሳጨትና ለመሸሽ ከመሞከር ይልቅ፤ ክፉ ልማድህን ፊት ለፊት ገጥመህ ለመጣል፣ ለማስወገድና ካንተ ለማራቅም ታጠቅ እንጂ!

በተለይ የወንድነት ልኩ፣ የአባወራነት ወጉ እንዲህ ነው!

ዋነኛው የእድገትህ እንቅፋት፣ የሥልጣኔህም መሰናክል ያ ወዳጆችህ ከብዙ ሥራዎችህ መካከል ለይተውና ነቅሰው እንድትጠራበት(ጥሩ እንድትኾንበት) የሚጠሩት ክፉ፣ መጥፎ ደካማም ምግባርህ!

ጠላትህም እርሱ እንጂ ነውና እንዲህ የለዩልህን ወዳጆችህን ስለጠሩበት ስሙ "ጠላቶቼ ናችሁ" ብለህ አትቆጣ፤ አትበሳጭም! እንደውም ባለዕዳ የኾንክላቸው ባለውለታዎችህ እንጂ ናቸው!

አባወራ

14 Feb, 16:05


መልአክነት ክዳኑ ጃንደርባነት ማገሩ ሰውነት ፈራሹ
================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ራሱን በመንፈሳዊነት ስም እንዲጥልና እንዲጠላ የሚነገረው ወገኔ፦ ከላይ ጣሪያ-መድረሻውን መልአክነት፤ አጥር ማገሩን ጃንደርባነት አድርጎ መኖር ወግ ይመስለዋል፤ ሆዳደር ምሁራኑ እንዲያ ይጮኹበታልና!

ሰውነቱን መለወጥ የማይችል መኾኑን እያወቀ፤ ነገር ግን የ"አውቃለሁ" እብሪቱ መልአክ መኾን እያስመኘ፣ በጃንደርባነት ሰውነቱን ሰልቦ ሐሞት የለሽ፣ ወኔቢስ ኾኖ ለባርነት ይተላለፋል።

ይህንን ሸፍጥ ሰምቶ፣ አምኖ፣ አክብሮ ከምንም በላይ ግን (በመምህሬ አትምጣብኝ፣ ተቋሜን አትነካብኝ እያለ) አምልኮ የሚከተላቸው ሆዳደር መምህራን ይሸጡለታል፤ ይገዛቸዋል፤ እርሱም ወደ ባርነቱ በፈቃዱ፣ ወደ ሞቱ በቁሙ ይጋዛል!

ወንድምዓለም! ለእኔ ያይደለ ለራስህ ስትል ለደንታህም ነገ አይቀርም!

አባወራ

14 Feb, 09:01


ገንዘብ ሙያ ጥበብም አልቸገረንም ሰው እንጂ
============================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ፕሮፌሰር፣ ዶክተር፣ ኢንጂነር፣ ወታደር፣ መምህር፣ የቤተክርስትያንም ሊቅ ሳይቸግረን፤ ሰው ያጣን፣ ሰው የራበን፣ ሰው የጠፋን፣ ወላድ የሰው መሃን ያደረገን ምንድን ነው?

ሰው እንዳይወጣን፣ ሰው እንዲጠፋን፣ ሰው እንዲቸግረን፣ ሰው እንዲርበን፣ ሰው እንዲናፍቀን፣ ሰው እንዲያጓጓን ያደረሰንስ ችጋር ምን የሚሉት ነው?

በሰው ተከበን ያውም በተማሩ በተመራመሩ፣ የምሁርነት ካባ-ላንቃ በደረቡ፣ ሊቅና ሊቃውንት መካከል ተከበን የሰው ያለህ ያሰኘን ምን ይኾን?

ከሰው እየተጋፋን፣ እየተረጋገጥንና እየተተረማመስን እየተገፈታተርንም፤ "የቸገረን ሰው ነው፣ የጠፋብንም እርሱ" ብንል ማን ያምነናል?

ወንድምዓለም! ለካስ የወለድናቸውን ቀርጥፈን የምንበላ፣ ያሳደግናቸውን የምናመክን፣ የደረሱትንም የምንሰልብ የሰው አጥፊዎቹ ከሰውም የወንድ ሰላቢዎቹ፦ እኛው ራሳችን ኖረናል!

እጃችንን በእጃችን፣ ልጆቻችንን በገዛ ራሳችን ያጠፋናቸው አይደለንምን? ከሰውነታቸው ይልቅ ገንዘብና ሙያ ጥበብም እንዲበልጥ የመከርናቸው እኛ፦

👉 ገንዘብ የሚያሳድዱ፣
👉 በሙያ የተካኑ አንቱታንም ያተረፉ፣
👉 መጻሕፍትን የጻፉ፣ ሲያስተምሩም አፍ የማያስከድኑ ሊቃውንትን አፈራን።

ነገር ግን፦

🌟 ተፈጥሮ ሰውነታቸውን የካዱ፣
🌟 ጸጋ ስጦታቸውን የጣሉ፣
🌟 መክሊት ማትረፊያቸውን የቀበሩ፣
🌟 ወንድነት ተፈጥሮአቸውን የሰለቡ ከሰውነት የራቁ፣ ሰው መኾን ያልቻሉ ኾኑብን እንጂ!

ታናሼ! ገንዘብ፣ ሙያ ጥበብም አልቸገረንም፤ አንድም የገንዘብ፣ የሙያ፣ የጥበብም እጦት አላፈረሰንም፤ ይልቁንስ ሰው ቸገረን እንጂ፤ አንድም ቀድሞ የፈረሰ ሰው፦ ትዳራችንን፣ ማኅበረሰባችንን፣ ተቋማቱን አፈረሰብን እንጂ!

ይህንንስ ማን አስተዋለ?

ሰውንስ እንዲህ ምን አፈረሰው?

አልጨረስኩም! ይቆየን እንጂ!

ነገ መቅረት አይደለም ማርፈድ አይቻልም!

አባወራ

14 Feb, 04:07


የተገፋች እውነት ትጣራለች ለራሳችሁ ስትሉ ኑና ስሟት!
===================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ትውልዳችን በተለይም ወንድሞቼ እንኳን እውነትን ኖሮ የሚያሳያቸው፤ እውነትን የሚነግራቸው እንኳ እያጡ ነው። የጠቀሟቸው መስሏቸው በዘመናዊነትና በመንፈሳዊነት ስም ለጆሮዋቸው ደስ የሚያሰኝ፣ ለስሜታቸውም የተጠነቀቀ ውሸትን ይግቷቸዋል!

ከዚህም የተነሳ ሰውነታቸው መጥፋቱ፣ ትዳራቸው መፍረሱ፣ ቤተሰባቸውን መበተኑ፣ ማኅበረሰባቸው የመማሰኑ ነገር እርግጥ ይኾናል።

እውነትን ሊነግሩን የተገባቸው፣ የሚገባቸውና የሚያገባቸው እነርሱ እንኳ ዘመኑ ካመጣው ንፋስ ጋር የሚነጉዱ፣ ከማዕበሉም የተነሳ የሚማቱ ኾነዋል!

የሰውነታችን መውደቅ፣ የትዳራችን መፍረስ፣ የቤተሰባችን መበተን፣ የማኅበረሰባችንም መማሰን ምክንያ ደግሞ፤ ጽድቅ የምንሠራበትን፣ ፍትሕ የምናሰፍንበትን ሰው የሚያደርገንን እውነት እርሱን ሳይኾን እነርሱ ላሰቡን የሚያበቃንን ውሸት ስለሚግቱን እንጂ!

የኾነው ኾኖ እውነት ዳስ ጥላ፣ ጣፋጭ ወይኗን ጨምቃ፣ ለዘመናት ትውልድን ያሳደገ፣ ያቆየና ያፋፋ ማዕድ አዘጋጅታ ኑ ከመጥፋታችሁ በፊት ሰውነታችሁን አግኙ ትላለች።

ተፈጥሮአዊ እውነትን፣ የመፍረሳችንን ምክንያትን፣ መድኃኒቱንም መስማት የምትሹ፣ እውነትን የምትወዱ ኑ ትላለች! ትጣራለች!

ወንድሞቼ! የ"አውቃለሁ!" እብሪት ካልወጠራችሁ፤ እንደኔ ባለው መሃይም መማርን ካልናቃችሁ ኑ!

እርሱም ደግሞ ለደንታችሁ እንጂ ለእኔ አይደለም!

እኔ ልሠራው የተሰጠኝን የምሠራ ባርያ ነኝ!

ማሳሰቢያ!
ቅዳሜ ልክ በ8:00 ሰዓት እንጀምራለን!

አባወራ

13 Feb, 14:01


አስገዳጅ የቅድመጋብቻ ሥልጠና ለሙግት አይቀርብም
==============================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

"አስገዳጅ የቅድመ ጋብቻ ሥልጠና አስፈላጊ ነው አይደለም" ብለን የምንሟገትበት ጊዜ የለንም። አስገዳጅ እንዲኾን፦

👉 ትዕዛዝ ተላልፎለት፣
👉 እርሱን የሚያጸድቁ ሹማምንት(በቤተክርስትያናችን) ተሰይመውለት፣
👉 የቴሌቪዥን ፕሮግራም ተፈራርመውለት፣
👉 ሥልጠና ተዘጋጅቶለት፣
👉 የሥልጠና መመሪያ ተደርሶለት፣
👉 አሠልጣኞች መሥሪያቤታቸውን አሟልተውና አስፋፍተውለት
👉 ከዚህ "ሥርዓት" የወጡት ተከልክለውለት፣
👉 በትዳር ያሉትም ቢያፈነግጡ ከሰበካ ጉባኤ እስኪባረሩ ተዝተውለት፣
"ሊቃውንቶቻችን" እኛን "የሚወዱንን" ልጆቻቸውን "ሊያገለግሉበት" እየተጠባበቁ ያሉበት ጉዳይ ነው።

እዚህም እዚያ፣ በመገናኛ ብዙኃንና በማኅበራዊ ትስስር ገጽ አንዳንድ "ለእኛ ሲሉ" ሌት ተቀን እረፍት ያጡ "ሊቃውንትና አገልጋዮች"፦ ቤተክርስትያኗ የቅድመ ጋብቻ ትምህርትን አስገዳጅ ልታደርግ ይገባታል፤ ፍቺው፣ ጾታዊ ጥቃቱ፣ ምኑ ቅጡ..." ሲሉ አትገረሙ። ተደርሶ የተሰጣቸው፣ ምንዳ የተሰፈረላቸው ከሞት አዋጁ በፊት የተላኩ ነጋሪት ጎሳሚዎች፣ መለከት ነፊዎች ናቸው።

ከዚያማ "የተለያዩ ተቀሟት፣ የማኅበረሰብ ክፍሎችና የዘርፉ ባለሙያዎች የቅድመጋብቻ ሥልጠና አስገዳጅ እንዲኾን ባቀረቡት አስተያየት፣ በሰጡት ጥቆማና ባደረጉት ሙያዊ ድጋፍ መሠረት ቤተክርስትያኗ ይህንኑ ማጽደቋን ተከትሎ ልጆቿ...."

ሮሚና እስትራቲ ሁሉንም ለእኛ ለኢትዮጵያውያን በተለይም ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን ካላት ከልብ የመነጨ ፍቅሯ የቢሊዮን ብር ፕሮጀክት ይዛ፤ የእንግሊዝ ቤተክርስትያን የፈረሰችበትን መንገድ በልካችን ጠርጋልናለች።

አትድከሙ!

ሁላችንም እያጨበጨብን የምንገባበት፣ አንዳንዶቻችንም "ምናለበት እንደ ካቶሊካውያኑ በሥልጠና በተገደድን(በተገደልን)" ብለን ባለማወቅ ባርነት-ሞታችንን የምንለምንበት ፣ ራሳችንን የምንጠምድበት፦ ወጥመድ ማለት እርሱ አስገዳጅ የቅድመጋብቻ ሥልጠና ነው!

🌟 እኔ የቅድመጋብቻ ሥልጠናን አስፈላጊነት ባምንበትም (እርሱንም ይዘቱ ይወስነዋል)
🌟 የትኛውንም ዓይነት አስገዳጅነቱን ግን እቃወማለሁ!

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን፦
እግዚአብሄር ደግሞ በሕዝቡ ላይ የሚኾነውን ሁሉ ያያል፤ ሆዳደሮች የተኛ፣ ያሸለበ፣ የማይሰማ፣ የማይነሳም መስሎ እስኪሰማቸው ድረስ ንስሃ እንዲገቡበት በሰጣቸው ጊዜ "የትዕግስቱን ባለጠግነት ይንቃሉ"!

ወዮልን! እኛ በዝምታችን ለተባበርናቸው ሁሉ!

"ውሸታም ነህ!" የምትሉኝ እናንተ፦ እባካችሁ፣ ስወዳችሁ፣ ስሞትላችሁም፤ እኔን ሰድባችሁ ኃጢያት ከምትሠሩ ጸልዩልኝ! የተናገርኩት ውሸት ኾኖ ለንስሃ እንዲያበቃኝ!

አባወራ

10 Feb, 08:00


እነዚህ ኃይለቃሎች፦
፩ኛ የጋብቻ ራስ እግዚአብሄር ነው
፪ኛ እንቢ ካልክ ከሰበካ ጉባኤ ትሰናበታለህ
፫ኛ የቅድመ-ጋብቻ ትምህርትን አስገዳጅ ማድረግ

የፕሮጀክት ድልድል የሮሚና ስትራቲ ሸፍጦች ናቸው። ቀሲስም ከእርሷ ስር ሠልጥነዋልና ዓላማዋን ሊያስፈጽሙ ተዋውለዋልና፣ እርሷም መስክራላቸዋለችና ይህንኑ ይነግሩናል!

እውን እነርሱ ከሮሚና ስትራቲ የተቀበሉት ወንዶቻችንን ለመስለብ ኾን ተብሎ የመጣ ፕሮጀክት ትዳራችንን ይታደግ ይኾን?

ኦርቶዶክሳውያኑ ትዳር-የለሽ፣ ዘር-አልባ፣ ልፍስፍስና አልጫ እያደረገስ ያለው ማን ነውና?

በአባቶቻችን ጊዜና ዘመን ጀግኖችን፣ ወላዶችን፣ ስታፈራ የነበረችው ቤተክርስትያን ዛሬ የወላድ መሃን ያደረጋት፣ ልጆቿ ትዳርን መመሥረት፣ ማቆምና መምራት አይደለም ራሳቸውን እንኳ መምራት እስካይችሉ ሆዳደርና አልጫ አልፎ ተርፎም የእናት ጡት ነካሽ ያደረገባት ትምህርት ምንድን ነው?

ጠይቁ ሞግቱ የጠመጠመን ሁሉ አትመኑ?

አባወራ

10 Feb, 06:50


እውነት ጽድቅ ፍትሕም ሲወድቁ ሰውነትን ያደቁ
============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

እውነት ጽድቅና ፍትሕ የምንጠብቃቸው፣ የምንኖርላቸው፣ የምናስተላልፋቸው፣ የምንሞትላቸው ሰውነትን የሚበይኑ፣ ለሰውነት የሚገበዩ፣ በሰውነት የሚሠሩ ናቸው።

ሆዳደርነት ጀብድ በኾነባት ዐለም፤ የመንፈሳዊውም ኾነ የአስኳላው ሊቅ ባስመሳይነት ባፍጢም በተደፋባት በዚህች አሁን በምንኖርባት ዐለም እነዚህ ሦስቱ ገበያ መሳቢያ፣ ሸማች ማጓጊያ፣ የነጋዴ ሱቅ ማሳመሪያ፣ የመድረክ ማስዋቢያ ኾነዋል።

ወገኔን በተለይም ደግሞ ታናናሾቼን ሊያስተምሯቸው የሚገባቸው ምሁራን፣ ሊያስተምሩት የተገባውን ተፈጥሮኣዊ እውነት፤ አንድም ስለ ምንዳቸወ፣ አንድም ደግሞ ስለሚኖሩት አልጫነት ሲሉ ይከለክሏቸዋል።

ኾኖም ደግሞ ባልሰጧቸው፣ ባልዘሩባቸው፣ ባላሠለጠኗቸው የእውነት፣ የጽድቅና የፍትሕ ጭብጥ "ፍሬያማ እንዴት አትኾኑም" ብለው ይወቅሷቸዋል።

እኔን! ወንድሞቼን!

አልጫነትን አጽድቀው ሲግቱን እንዳልነበሩ፤ ዛሬ ትውልዱ ፈዟል፣ ደክሟል፣ ባክኗል፣ ማስኗል ይሉናል። ጀግንነትንና ጀግናን፣ ወንድነትንና አባወራን ንቀውና አቃለው፤ የዘሩብንን አልጫነት እንጂ ሌላ ምን ልንሰጣቸው ኖሯል!

እውነት፣ ጽድቅ ፍትሕም እንዲናቅ፣ እንዲገፋና እንዲወቅ ሊቃውንቱ ሲያስተምሩና ሲያለማምዱ፤ አባታችን የሰጠንን ሰውነት እየናዱ መኾኑን አያውቁምን?

አልጨረስኩም... ቅዳሜ እመለስበታለሁ እንጂ!
ወንድምዓለም! ብዙዎቻችንን እንዳንለወጥ እግር ከወርች ጠፍሮና ጠርንጎ ያሰረን የ"አውቃለሁ" እብሪት ካልያዘህ ና ብዙ የማወጋህ አለኝ!

ደግሞ የምትመጣውም ለደንታህ እንጂ ለሄኖክ እንዳይደለ አትርሳ!

አባወራ

08 Feb, 06:12


ጠብቆትህ አያስፈልግም ያሉትን ባርነቱን አይወቅሱም
===============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ትናንት በጽድቅ ስም መሠረታዊ፣ ተፈጥሮአዊና ሰዋዊ የኾነ እውነትን አጣመን ያስተኛነው(የሰለብነው) ትውልድ ዛሬ በጩኸት (በjumperም) አይነሳም!

ይህ ትውልዱን ከእውነት የማራቅ፤ ይህንኑም በዘመናዊነትና በጽድቅ ስም መጋት እንደቀጠለ ነው፤ ከዚህም የተነሳ ወገኔ ከተፈጠረለት ዓላማ፣ ከተለየለት ሚና ርቆ ይባዝናል!

መሠረታዊ በተለይም ተፈጥሮኣዊ የኾኑ እንሰሳት እንኳ በደመነፍሳቸው አውቀው፣ ለይተው፣ ጠብቀውና አስጠብቀው የሚጠቀሙበትን እውነት መካድ፤ ክዶም ማስተማር ትውልድን መግደል፤ ሰውነቱንም መሻር ነው!

ልክ የዛሬ ሳምንት የካቲት 8 2017 ዓ.ም. ከቀኑ ከስምንት ሰዓት ጀምሮ ከመጽሐፋችን ተነስተን እንወያያለን።

አጀብ፣ ጭብጨባ፣ ዴኮርና ካባ የሌለበት እውነትን ያለ ማዋዣ ፍርጥ አድርገን የምንወያይበት የወንዶች ጉባኤ ይኾናል!

ማሳሰቢያ!
ስትመጣ ለደንታህ እንጂ ለሄኖክ ብለህ አይኹን!

አባወራ

07 Feb, 06:12


እግር ቆርጠው ሩጡ እጅ ነስተው ጨብጡ
==========================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ተወልደው ያደጉ፣ አድገው ድክ ድክ ሲሉየነበሩ ልጆቻችን ዛሬ በመሮጪያቸው፣ ዛሬ በመዝለያቸው፣ ዛሬ ለጽድቅና ለፍትሕ በሚፋጡኑበት ጊዜያቸው ሩጫቸው፦

👉 ለምን
👉 በማን
👉 እንዴትስ ተገታ?

ዛሬ ወገኔን በተለይም ወንዱን በሩቅ እጅ ነስተው ሲያበቁ ፈዟል፣ ደንዝዟል ማለትንስ ምን አመጣው?
የሚሠራበት እጁን የሚሮጥበት እግሩን ማን ነሳውና
👉 ለእውነት ግድ የለሽ፣
👉 ለጽድቅ ዳተኛ፣
👉 ለፍትሕም ደንታቢስ ኾኗል ብለው ያሙታል?

ጉድ እኮ ነው! ግራ የገባ ነገር፦
እግር ቆርጠው ሩጡ
እጅ ነስተው ጨብጡ እያሉ ማደናገር
ያውም ከተማሩት ከሊቃውንቱ መንደር!

የካቲት 8 2017 ዓ.ም. እንፈታዋለን

አባወራ

06 Feb, 07:14


ሰው ሳይኮን በቅጡ መልአክነት መ^ቀላወጡ
================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

የዘመኔን ትውልድ በተለይም መንፈሳዊ መኾን፦ በመንፈሳዊነቱ አባቱንና አምላኩን ማወቅ፣ ባወቀውና በገባው ልክም መኖር ፈልጎ ብዙ ከሚያባክኑት ርቆ የመጣውን ወንድሜን ምን አጠፋው አትሉኝም?

በሉኛ?

በቅጡ ሰው ሳይኾን መልአክነትን እንዲቀላወጥ መማሩ!

ከሰውነት ልክ፣ በሰውነት ቅጥ፣ በተለይም በወንድነት ቁና በአባወራነት ግርማ በመከራ ተጠቅጥቆ፣ ተሰፍሮ፤ በዋናነት ለመጣበት ዓላማ ሲቀጥል ግን ለራሱ፣ ለሚስቱ፣ ለልጆቹ፣ ለቤተሰቡ፣ ለማኅበረሰቡ፣ ለቤተክርስትያንና ለሀገር ይተረፈረፍ የነበረው ወንድሜ፤ መልአክነትን የመንፈሳዊነት ግብ አድርገው በጋቱት መምህራን ከሰውነት ራቀ፣ ወደቀ፣ ደቀቀ፣ ....።

ይህ ሰው ኾኖ ተፈጥሮ ራስን እንደ መላእክት መቁጠር በተለይ ካቶሊካውያን ዘንድ የተለመደ መጀመሪያ ካህናቱን ሲቀጥልም ማኅበረ ምዕመኑን አልጫ ያደረጉበት መንገድ ሸፍጥም ነው!

በተለይ ከደርግ መውደቅ በኋላ የመጡ፣ ቀድመው የነበሩና ያንሰራሩ(እንደ ሰንበት ትምህርት ቤቶቻችን ዓይነት) ትውልዱ ሰው ሳይኾን በቅጡ መልአክነትን እንዲናፍቅ፣ እንዲስል፣ እንዲመኝ፣ እንዲለማመድ አድርገውታል።

ስለኾነም ወገኔ በሰውነቱ የተሰጠውን ጸጋ ቀብሮ፣ ከሰውነት ግብርና ምግባር ርቆ፣ ከሰው ጋር እየኖረ ሰውነት ባሕርዩን ክዶ ከመላእክት ወገን ለመደመር፣ ለመቆጠር፣ ይናፍቃል! ሲያምረውም ይቀራል እንጂ መቼም አይኾንም!

ሲጀመር መልአክነት የሚያስመኝ ምንም ነገር የለም!

የማይኾን፣ የማይቻል፣ የማይጠበቅ፣ የማይደረግ ነገር ይቻላል ብለውት፤ ራስ ማንነቱን አስኮንነውና አስጥለው መልአክነትን አጽድቀው አስናፍቀው ግተውት፤ ከሰውነት ተርታ፣ አባቱ ሊያድነው ወዶና ፈቅዶ ከለበሰው ስጋ፣ በሚመለክበት እሪና ካስቀመጠውም ሰውነቱ ለይተውት ሲያበቁ፦ ሰው ኹን ይሉታል!

እንዴት ይኾናል?

ወንድሜን! እኔን!

የሚደንቀው ነገር ሰውነቱን በሰውነቱም ያለ ጸጋ ሰጦታውን፣ በተለይም በወንድነቱ ተለይቶ የተለገሰውን ወንድነት መክሊቱን፦ እንዲንቅ፣ እንዲጠየፍ፣ እንዲለይ፣ እንዲጥል፣ እንዲቀብር ካደረጉት በኋላ በእነርሱ ሊፈጽማቸው የነበሩትን ጽድቅና ፍትሕ ከእርሱ ይጠብቃሉ።

እነርሱ በጽሑፍና በመጻፍ በመድረክም ማላዘናቸው አይቀርም እኮ! ነገር ግን የሚጮኋትን መሬት ላይ አውርደው አይሠሯትም፤ በጣታቸውም አይነኳትም!

ግራ ተጋብቶ፣ ግራ ገብቶትም ወንድሜ ዝም ቢል! "ትውልዱ ፈዛዛ ነው! ደንዛዛ ነው! ይሄ ትውልድ እንኳን ተነገሮት እንዲህና እንዲያ ቢደረግም አይገባውም! ይበለው!" ይላሉ።

ታናሼ! ወንድሞቼን ስለ ሰውነት ከምንም በላይ ግን ስለ ወንድነት ማን ነገራቸው? ሌላውን ቅጥያ ተውትና "ሰው" የመኾንን ኩነት፣ በተለይ ደግሞ "ወንድ" የመኾንን ልዩነትንስ ማን ዐሳያቸው!

ወንድነታቸው በዚያም ያሉ ባሕርያት የኃጢያት ምክንያት እንጂ ጽድቅ መፈጸሚያ መሣሪያ መኾናቸውን ምን ያክሎቹ ተማሩ! እንዲያ መኾኑንስ ካወቁት ምን ያክሎቹ በእነርሱ ላይ ሠለጠኑ አበለጸጓቸውም!
ብዙዎቹ መልአክነትን የሚናፍቁ አይደለምን!

ግን ለምን?

በቅጡ ሰው ሳንኾን? ውጤቱስ ምን ሊኾን?
ቅዳሜ የካቲት 8 2017 ዓ.ም. ኑና ራሳችንን እንፈትሽ!

አባወራ

05 Feb, 09:04


ትኩረት ያጣው የወንዱ የአባወራውም መራቅ ከቤተክርስትያን
======================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

"ይህ ለምን ኾነ?" ብሎ ከመጠየቅ ይልቅ ሴቶች ከወንዶች ይልቅ መንፈሳዊ፣ እናቶች ከአባቶች ይልቅ ጸሎተኛ እንደኾኑ ይነግሩናል።

ይህ ፍጹም ከእውነት የራቀ ነጭ ውሸት ነው!

ይህ በተለይ ከወንድነታቸው ተለይተው፣ በወንድነት ከተሰጣቸው ጸጋ ርቀው፣ ወንድነት መክሊታቸውን ፦
💪 እውነት
💪 ጽድቅ
💪 ፍትሕን ባፍና በመጣፍ አይደለም በተግባር ከማሳየት ይልቅ ቀብረውት የሚኖሩት ወንዶች ይበልጡንም የቤተክርስትያን "አገልጋይ ነን" የሚሉ ምስኪናን አልጮች የሚናገሩት ነው።

እነርሱ ሲያውቁ ከእነርሱ ሌላ፣ ከእነርሱ በላይ፣ ከእነርሱ ውጪ አዋቂ ጠማቂ ያለ የማይመስላቸው፣ ከሌላውም ውድቀት መማር የማይፈልጉ እነዚሁ ጥቂት ሰዎች፤ ትውልዱ አባቱ የሰጠውን ተፈጥሮ አውቆ፣ ባወቀው ማንነቱ ላይ ሠልጥኖና በልጽጎበት ስለ እውነት፣ ጽድቅና ፍትሕ እንዲኖር አይፈልጉም!

ይልቁንስ እውነት በተሰቀለችበት አደባባይ፣ ጽድቅ በተሻረበት መንገድ ላይ፣ ፍትሕ በጠፋበት ችሎት ላይ በመንፈሳዊነት ስም "ሆደ ሰፊ፣ ነገር አሳላፊ ነኝ" የሚል አልጫ እንዲወጣው አሰስነቱን አጽድቀው ቢግቱት እንጂ!

ወንድምዓለም! በምታስቀድስበት፣ ከቤተሰብህ ጋር ምስጥራትን በምትቀበልበት ቤተክርስትያን የወንዶቹ በተለይም ደግሞ የአባወራዎቹ ቁጥር "ለምን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየሳሳ መጣ ብለህ ጠይቅ?" !

"ወንዱ ኳስና ፊልም፣ ድራፍትና አረቄ፣ ጫትና ቁማር፣ ሥራና ትምህርት... እያታለለው ነው" እዪሉ ለስንፍናቸው ሰበብ ሲደረድሩ "እውነት ነው" ብለህ አትቀበል።

ቤተክርስትያን እንደ ተቋም መሥራቿ እንደኖረው፣ ተከታዮቹም እንዳስተማሩት እውነት የሚነገርባት የእውነትስ ተምሳሌት ኾናለች ወይ?

ጽድቅ የሚሰበክባት ጽድቅ በተግባር የሚገለጥባት ቤቱ ኾናለች ወይ?

ፍትሕን የሚያውጁባት ፍትሐዊ ፍትሕ ጠያቂም ኾናለች ወይ ብለህ ጠይቅ?

ወደድክም ጠላህም ወንዱ ምን ማጅራት መቺ፣ ሙሰኛና፣ ሴሰኛ፣ ሱሰኛም ቢኾን ሕሊናው ልክ እንዳልኾነ ሲነግረው፤ ይህንኑ ከንቱ ማንነቱን ስለ ገንዘቡና ስለ አጀቡ ብለው ትተውለት እያቆለጳጰሱ የሚጠሩትን ይሸሻል።

ራሱ የሚጠየፈውን፣ ሊያስወግደው ፈልጎ የፈተነውን፣ ከሕሊናው ጋር የሚዋቀስበትን ኃጢያቱን ይዞ ሲመጣ እነርሱን ከእርሱ የበለጠ በትጋትና በጥራት በብቃትም የሚሠሩት፣ እርሱን "ጻድቃን" እያሉ የሚጠሩት፣ የሚሰብኩትን እውነት ሳይኾን ፍርሃትን እንደጽቅ የተከናነቡት "አገልጋዮች" ዘንድ መሄድ ይሞግተዋልና ይርቃል።

አንድም ደግሞ ከክፉ ምግባር ተለይቶ ወደ እውነት የሚጠጋው፣ ለጽድቅ የሚቸኩለው፣ ፍትሕ ለሚጠማው አባወራ ደግሞ ከዐለም የባሰ የጥፋት ሥራን በዚያ ቢያይ ይሸሻል።

አንድም ደግሞ በተፈጥሮው ላይ ሠልጥኖ እውነትና ጽድቅን ታጥቆ ለፍትሕ የሚቆመው ሰው በሙስና፣ በሴሰኝነት፣ በዘረኝነትና በሆዳደርነት ሰምጠው የሚዋኙ "አገልጋዮች" ግብራቸውን እንዳይገልጥባቸው የተለያየ ስም ለጥፈው ያሸሹታል፣ ያርቁታል፣ አልፎ ተርፎም ያባሩታል!

ወንድምዓለሜ! ወንዱ ከቤተክርስትያን በተለይም አባወራውን ከጉባኤ መካከል ብታጣውና ማኅበሩ በሴቶችና እናቶች አልያም ለሴትነት የቀረቡ፣ ከሴቶች ውዳሴና ይኹንታ በሚፈልጉ ምስኪናን ወንዶች ተሞልቶ ብታየው፦ ወንዱ እንጂ ሴቶች በተለይም እናቶች መንፈሳዊ ናቸው፤ አትበል!

ምዕራባውያንም ይህ እውን መስሏቸው ወንዶቹን ጥለው በተለይም ድንበር የሚጠብቁ፣ ሕግ የሚያረቁ፣ ትውልዱን የሚያነቁ፣ ለጽድቅና ለፍትሑ አደባባይ በእውነት የሚያበቁ፣ እነርሱንም ግድ የሚሉ፣ የሚሞቱላቸውንም አባወራዎቻቸውን ጥለው ሴቶችንና እናቶችን ተኮር "ዐውደምኅረት" ዘርግተው ነበር!

ውጤቱ ግን አላማረም! ወንዱ ቤተክርስትያኑን ጥሎ ወጥቶ፣ ካህናቶቻቸው ሴት እስኪመስሉ፣ በሴቶች ካህናት እስኪተኩ፣ ቀሪዎቹም ግብረሰዶማዊ እስኪኾኑ ድረስ የማኅበረ-ክርስትትያኑ መልክና ቅርጽ ተቀይሯል። መቼም አሁን የደረሱበትን ውጥንቅጥ ላንተ አልነግርክም!

ይህ በተጨባጭ ማስረጃ በጥናትም የተደገፈ ደረቅ ሐቅ ነው! ቢመርህም ትማርበት ዘንድ ዋጥ አድርገው! ዛሬን በምንቸገረኝነትና በግዴለሽነት ያለፍነው ሁሉ ነገ እንዲህ መኾኑ አይቀርም!

ወንዱ በተለይም ቤቱን፣ ቤተሰቡን፣ ሚስቱን፣ ልጆቹን፣ ማኅበረሰቡን፣ ቤተክርስትያኑን፣ ሀገሩን የሚመራው አባወራ ከአባቱ ቤት ከቤተክርስትያን ሲርቅ(ኾን ተብሎ እየተደረገ ነውና) ያን ጊዜ ትውልዱ ያስተውል!

እነዚህ ሦስቱ ከሀገር ይጠፋሉና፦
💪 እውነት፣
💪 ጸድቅና
💪 ፍትሕ!

እነርሱን ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ቢፈልጓቸውም ቅሉ፤ እነርሱን ማወቅ፣ ማሳወቅ፣ መሠልጠን ማሠልጠንና ከትውልዱ ግድ ማለት ግን እልህ አስጨራሽ፣ ሰምዓትነት የሚያስከፍል የሚገባቸውም የወንዱ በተለይም የአባወራው ድርሻ ነው!

ነገር ግን ወንዱን የሚያሳድገው ወደ አባወራነት ልዕልና የሚያወጣን ጭብጥ ሳይሰጡት ፍሬ ፈልገውበት ትውልዴን ማስጨነቅ፤ የራስን ጥፋት ተጠያቂነቱንም በእርሱ ለማላከክ እንጂ ሌላ አይባልም!

ትውልዴ በተለይም ወንዱ ወንድሜ፦ ወንድ ከወንድም የወንድ ቁና አልፎ ደርሶም አባወራ እንዲኾን፤ ለተፈጠረለት እውነት፣ ጽድቅና ፍትሕ እንዲኖር ማን አስተማረው?
👉 ይህንን ማን ያሳየው?
👉 ጭራሽ ደግሞ ይህንኑ ችግር ከድጥ ወደ ማጥ የሚከት ወንዱን ከሴቷ፣ አባወራውን ከሚስቱ፣ ልጅትን ከአባቷ የሚነጥል፣ ወንዱን ወቅሶና ከሶ ተፈጥሮኣዊ ጸጋውን የሚኮንን ማርክሳዊ ኮሚኒስታዊ ሸፍጥ በሥልጠና መልክ መጣ እንጂ!

አንድም ደግሞ እውነት፣ ጽድቅና ፍትሕን ለዓለሙ ሊያሰተምሩ፣ ሊያሳዩ የሚገባቸው መምህራን አልጫነትን፣ ሰበበኛነትን፣ ስንፍናንና ስሜታዊነትን በጽድቅ ስም አስታከው በፍርሃት ሲደበቁ ያን ጊዜ ወንዱ አባወራውም ቤተክርስትያን የሚሄድበትን ምክንያት፣ የሚኖርለትን ትርጉም ያጣዋል!

ወንዳዊ የኾነ ተፈጥሮው፣ አባታዊ የኾነ የአምልኮት መዋቅሩ በእንዲህ ካለ ከባሕርዩ በተለየ፣ ሊሠራበት ከተሰጠው ጸጋ፣ ለሚኖርለት ከታጠቀው መክሊት ጋር በተጣረሰ ምግባር አይጸናምና!

ታናሼ! አውርቶ አደር አውሪ፣ "ብዬ ነበር" ጯሂ ወንድሞቼን ተጠያቂ ማድረግ አይችልም! የምታወራውን ኑር! የምትጮኸውን ሥራ! የምታስተምረውንም እውነት በተግባር ዐሳይ! አን ተ በጣትህ የማትነካውን ጩኸት ተቀብሎ ቢጮህልህ እንጂ ማንም አይሠራውም!

አለበለዚያ ባለቤታቸው እንድትሰበስባቸው፣ እንድትጠብቃቸው፣ እንድታሰማራቸውም የሰጠህ በጎች በተኩላ እየተበሉ ይመነምናሉ፤ አልያም ሲባዝኑ ይበተናሉ።!

ያንጊዜ "ጮኬ ነበር፣ ተናግሬ ነበር..." ብሎ ማላዘን ሰበበኝነት ብቻ ይኾናል! ቤታቸውን፣ ቤተሰባቸውን፣ ሚስቶቻቸውን፣ ልጆቻቸውን፣ ሀገራቸውን ለሚመሩት ወንዶች ቦታ ላልሰጠች፤ በተለይ ደግሞ ወንድነት መክሊታቸውን እየኮነነች ለመጣች ቤተክርስትያንም ኾነ ባለድርሻ አካላት መልዕክቴ ነው! ነገ ሴቶቹም ይቀራሉ ባዶነትም የማይቀር ይኾናል!

"ተናግሬ ነበር" ለማለት አይደለም! በተግባር ለሚፈልጉት ወንድሞቼ እያሠለጠንኩ እንጂ! "አውቃለሁ..." የሚለው እብሪትህ ካልገደበህ ወንዱ በተለይም አባወራው ከእውነት ጽድቅና ፍትሕ ተገፍቶ ፍዝ የኾነበትን መንገድ የካቲት 8 እነግርሃለሁ ይቆየን!

አባወራ

04 Feb, 04:17


https://youtu.be/lypcc5g8lJY?si=zoKXpLSxOoFf0MIx

አባወራ

04 Feb, 03:51


https://youtu.be/s-vL0mHUQKg?si=CFtDVO9nThX279sQ

አባወራ

03 Feb, 14:00


የሙክት አውራ የስልብ አባወራ የለውም
=========================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

🌟 ምን ዓይነት ተላላ እረኛ አልያም ደግሞ ሆዳደር ምንደኛ ነው በጎቹን አኮላሽቶ ለርቢ ተስፋ የሚያደርጋቸው?

🌟 ምን ዓይነትስ ሞኝ እረኛ አልያም ደግሞ ሆዳደር ምንደኛ ነው በጎቹን ሰልቦ ሲያበቃ አውራ አለኝ ብሎ የሚኮራው?

🌟*ምን ዓይነት ጅላጅል እረኛ አልያም ደግሞ ሆዳደር ቅጥረኛ ነው ኮርማውን አኮላሽቶ ከላሟ ጥጃና ወተት የሚጠብቀው?

🌟 ሰንጋ ፈረሱንስ ቀጥቅጦ ሲያበቃ እርሱን የመሰለ ውርንጫ ከጋጣው የሚጠበቀውንስ?

🌟 የሙክት አውራ የስልብስ(የጃንደርባስ) አባወራ አለውን?

🌟 ምን ዓይነትስ ሞኝ አባት አልያም ደግሞ ሆዳደር አደራ-በል ነው ልጆቹን፦
👉 ወኔያቸውን ሰልቦ፣
👉 ሐሞታቸውን አፍስሶ፣
👉 ልባቸውን አጥፍቶ ሲያበቃ እውነትን፣ ጽድቅንና ፍትሕን ከምግባራቸው የሚጠብቀው?

ሁሉም የካቲት 8 2017 ዓ.ም. ይጠባበቃሉ!

አባወራ

03 Feb, 04:11


አሰስነቱን ላጸደቁለት ውድቀቱን እብሪቱ ይቀድመዋል
================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ሆዳደሮች ሊበዘብዙት ያሰቡትን ምስኪን ትውልድ አልጫነቱን፣ ሰበበኛነቱን፣ ስንፍናውንና ስሜታዊነቱን ከመንፈሳዊነት መድበው ጽድቅ አድርገው አቆለጳጵሰው ይግቱታል።

ብዙውን ጊዜ እነዚህ ሆዳደሮች ያልተማሩ መሃይሞች፣ ፊደል ያልቆጠሩ ጨዋ፣ ንባብ ያልዘለቁ ተራ እንዳይመስሏችሁ። ይልቁንስ አንብበው አዋቂ፣ ተምረው መምህር፣ አስመስክረውም ሊቅና ሊቃውንት የኾኑ እንጂ።

ጠላትም መንጋውን ወደ ባርነት በረቱ ሊያግዝ ወዶ ፈልጎ የሚቀጥራቸው እንዲህ የተማሩ፣ ያወቁና የነቁ የተባሉትን፤ ትውልድ ያነቁ ዘንድም እድልም፣ ጆሮም፣ መድረክም፣ ልብም የሚሰጣቸውን ነው።

ስለኾነም እነርሱ ለምንዳቸው ሲሉ መንጋውን በደመወዝ ለቀጠራቸው የሚያሰቡበት ኾነኛ መሰሪ ቀለቡ ትውልዱን አሰስነቱን እያጸደቁ በመንፈሳዊነት እየለወሱ በመጋት ነው።

እርሱም አምኖ በሚከተላቸው፣ አንግሦ በሚታዘዛቸው፣ በማይሞግታቸው "እረኞቹ" እጅ ሲወድቅ፤ ሆዳደሮቹ እነርሱም ለጠላቱ ሲሳይ ይኾን ዘንድ ይሰዉታል፣ ይበልቱታል ያመቻቹታልም፤ እንዲህም ያደረጉት ዘንድ ፈቅዶላቸዋልና።

ከዚህ ውድቀቱ በፊት፣ ባፍጢም ከመደፋቱም ቀድሞ፣ ወዳጆቼ ባላቸው ከመሸለቱ አስቀድሞ አስጠንቅቆ ነጋሪ፣ ነቢይ መካሪ ቢላክለትም ግን የመስማቱ እድል እጅግ ጥቂት ወይንም ጭራሹንም እምቢተኛ ይኾናል።

እርሱ ከምስኪንነቱ በሚነሳ አውቃለሁ የሚለው እብሪቱ፤ መልካምና ክፉን የሚለውን ልቡን ለማሠልጠን ካለበት ዳተኝነቱ የተነሳ በሰሙ ሆዳደሮቹ እረኞች ነድተው ለተኩላ ይሰጡታል ብንልም ቅሉ፤

እውነቱ ግን ከሆዳደሮች እግር፣ ከጠላቱ ማዕድ፣ ከተኩላውም መዳፍ የሚጥለው ይኸው "አውቃለሁ" ብሎ ከጥበብ ይልቅ፣ አንድም ጥበብ ከሚቀዳበት ምንጭ ይልቅ የሚሸረሸር፣ የሚፈርስ መጩለቂያ ፉካውን ያስመለከው እብሪቱ ነው።

ወንድምዓለም! አሰስነትክን አጽድቀው በመንፈሳዊነት ስም ሲግቱህ ከሰውነት ወደ መላእክትነት እየተሸጋገርክ እንዳይመስልህ ሲጀመር አትኾንም አይቻልህምና፤ ይልቁንስ ሆዳደሮች ሊያርዱህና ሊያወራርዱህ እንደ ፍሪዳ እያደለቡህ እንደ ሙክትም እያሰቡህ እንደኾነ አስተውል እንጂ!

አስተውል! አሰስነቱን ላጸደቁለት ምስኪን ውድቀቱን እብሪቱ ይቀድመዋል! ምስኪንን ለጠላት ምራቅ የሚያስውጥ አድርጎ ከሆዳደሮች እጅ፣ ከጠላትም እግር ስር አስብቶ የሚጥለው ይኸው "አውቃለሁ" የሚለው እብሪቱ እንደኾነ የአባወራ ሥልጠናችን በቂ ምስክር ነው!

አንተም አውቃለሁ የሚለው እብሪትህ ካልቀደምህ፤ በትምህርት ታናሽህ ከኾንኩት ወንድምህ መማር ነውር ካልኾነብህ የካቲት 8 2017 ዓ.ም. እጠብቅሃለሁና ና!

አባወራ

30 Jan, 14:05


መሠረቱን አናግተው ጡብ መደረድር እንዲፈርስ እያደር
==================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ተፈጥሮአዊ እውነቶች፣ ተቋማትና ማኅበረሰብ የተገነቡባቸው እሴቶች በዙሪያችን ሲፈራረሱ በግዴለሽነታችን ጭብጨባ፣ በዝምታችን ትዘባ፣ በለቅሷችን "እልልታ" ታጅበው ነው።

እንደ ግለሰብ፣ እንደ ቤተሰብ፣ እንደ ማኅበረሰብ፣ እንደ ተቋም፣ እንደ ሀገር... መፍረሳችን ለእውነት ካለን ደንታቢስነት፣ ውስጣችን ጠፍቶ ከቀዘቀዘው ፍም የተነሳ እንጂ በአፍራሾቹም ኾነ በመራጃቸው ጥንካሬ አይደለም።

ይህንን የማፍረሱ ሥራ በዋናነት የሚሠሩት እንደ እኔ ያልተማሩ መሃይማን አይደሉም፤ ይልቁንስ ማስትሬትና ዶክትሬት የጫኑ፣ ሊቅና ሊቀ-ሊቃውንት የተባሉ ምሁራን እንጂ።

ይህንን ደግሞ ቁሳዊ ሥልጣኔያቸውን ከማኅበረሰባቸው፣ ተቋማዊ ግንባታውን ከትውልድ-ልጆቻቸው፣ ዝናና ገንዘብን ከፈጣሪያቸው አስበልጠው የወደዱ፤ ስለ ቀደሙትም የኋለኞቹን የሰዉ ያፈረሱ ምዕራባውያን ምሳሌዎቻችን ናቸው።

ለዚህ መፍትሔ እንቅፋት የሚኾነው ትውልዱን አስቀድመው እውነት የኾነ እውቀትን፣ መድሐኒት የኾነ ጥበብን ሳይኾን ራሳቸውን "እውነትና ጥበብ" አድርጎ እንዲቀበል አድርገውታልና ከድጥ ወደ ማጥ ሲከቱት ፍጹም እያመናቸው መኾኑ ነው።

በዚህ ወቅት ለትውልዱ አርነት የሚወጣበትን እውነቱን፣ እውነት የኾነ እውቀቱን መንገር ወንጀል ይኾናል። ከድጥ ወደ ማጥ የሚሰምጠው ትውልድም ከማጡ ሰምጦ ከመቅረቱ በፊት እውነት የሚነግሩትን ኮንኖ ሆዳደር ቀባሪዎቹ መብላት መጥገባቸውን እርግጠኛ ኾኖ ጥፋቱ ይፈጸማል።

ወንድምዓለም! ለእውነት፣ እውነት ለኾነ እውቀት፣ ማኅበራዊ ለኾነም እሴት ግድየለሽ ከኾንክ ነገ ሀገር፣ ማኅበረሰብ፣ ቤተሰብ፣ ትዳር፣ ትውልድም እንደማይኖረን አስተውል!

መሠረታችን እየተሰነጠቀ ነው! ማኅበረሰብና ተቋማት የተገነቡበት ውሃ ልክ እየተናጋ ነው። የፍቺያችን(የትዳሩ) መጨመር፣ ከጋብቻ ውጪ የሚወለደው መበራከት፣ በወንድና በሴቱ መካከል እያደገ የመጣው አለመተማመን የእነዚህ ውጤት ነው።

ኾኖም ግን ለኾነብን፣ እየኾነብን ላለውም ኾነ ለሚኾንብን ማንም ላይ ጣትህን አትጠቁም፤ "እኔ ምን እያደረግኩ ነው" ብለህ ጠይቅ እንጂ!

መሠረት እያናጉ ጡብ እንደርድር የሚሉትን በግዴለሽነት በዝምታም ማለፍ ትውልድ እያደር እንዲፈርስ ሰውነቱንም እንዲያጣ መተባበር ነው።

አባወራ

30 Jan, 03:22


https://youtu.be/96-aQlo6AtI?si=Mf8VklCV4OxYBb37

አባወራ

29 Jan, 14:00


ፍቺ ጀብድ ዲቃላ መጎተት ጀግንነት ሽርሙጥናም ክብር አይደለም
=========================================

አንቺ የውብ ዳር!

አንድ ወንድምሽ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ በልምድም በስሎ ያተረፋቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሻል፤ አንቺ ግን በወደድሽው ኑሪ!

ፍቺ፣ ዲቃላ መጎተት፣ ሽርሙጥና ሦስቱም የጋራ የኾነ መነሻ መገለጫም ጠባይ አላቸው፤ እርሱም አመጸኝነት ነው። በመጀመሪያ በአምላካዊ ትዕዛዙ ላይ፣ ሲቀጥል በአባታዊ መዋቅሩ፣ በሦስተኛም በአባወራዊ ቅጡ ላይ የተነጣጠረ አመጽ።

በዚህም ትውልድ መረን ሲወጣ ማኅበረሰብ፣ ሀገርና ቤተክርስትያንም ይፈርሳሉ። ይህንን ደግሞ ከሴቶች ይልቅ ኃላፊነታቸውን የረሱ፣ ግዴታቸውን የዘነጉ፣ ሚናቸውን የሳቱ ወንዶች ያቀላጥፉታል።

መቼም ከዜና አትርቂምና የዚህን ግማሽ ዓመት የፍቺ ቁጥር ሳትሰሚው አትቀሪም። እርሱ ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት በ34 ከመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ብቻ ሳይኾን ጋብቻ ራሱ አምና በተመሳሳይ ወቅት ከነበረው ሰባት በመቶ መቀነሱንም ጭምር እንጂ።

ይህ እጅግ አስደንጋጭ ዜና ነው። ሁላችንንም እጅግ በጣም ሊያሳስበን የሚገባ። ትውልድና ሀገር በማስቀጠሉም ረገድ በርካታ የቤት ሥራ እንዳለብን የሚያመለክት።

ኾኖም ግን ይህ ዜና ማንን አስደነገጠ? ዜና ኾኖ ከማለፉ፣ የወሬ ግብዓት ኾነ ከመውጣቱ፣ የጨዋታና ቧልት ማድመቂያ ከመኾኑ ባለፈ፦

👉 ወላጆችን አስደንግጧልን?
👉 ዛሬ ያልተፋቱ ባልና ሚስትንስ አሳስቧልን?
👉 የቤተክርስትያን አባቶችንስ፣ የሀገር ሽማግሌዎችንስ "ምን ተሻለን" አስብሏልን?
👉 የትዳር መካሪ፣ አማካሪና አሠልጣኞችንስ?
👉 መምህራንንስ?
👉 የመንግሥት አመራሮችንስ?

እህትዓለሜ! ፍቺ ቅሌት ውርደት እንጂ ጀብድ አይደለም፤ ኾኖም አያውቅም! ዲቃላ መጎተትም እንዲሁ ነውር ሲኾን፣ ሽርሙጥናም አሳፋሪ፣ ኃጢያትም እንጂ
የሚያስመካ የሚያኮራም አይደለም!

በእርግጥ የሚኖሩትን አልጫ ሕይወት አጽድቀው የሚመክሩ፤ አይደለም ከዐለሙ፣ ከቤተክርስትያን ያሉ መምህራን እንኳ፤ ፍቺን መፍትሔ እንዲኾን አቅልለው መማር፣ ማስተማራቸው እርሱን እያባባሰው መጥቷል!

ከምንም በላይ ደግሞ አጉል ዘመናዊነትን ከመንፈሳዊነት አዋደው፤ የወንድና የሴት ሚናን ደበላልቀው፣ ማስተማር ዛሬ ከቤተክርስትያን ሠርጎ ገብቶ ኖሯል፤ ልጆቿ ላይ ጨክና እርሷው እናታቸው እንደ መርሕ የምታስተምረው መኾኑን ሳይ እቆጫለሁ።

ይህም ከመቼውም ጊዜ ለበለጠ ፍቺ፣ ጋብቻን ፍራቻና ከጋብቻ ውጪ መውለድ መስፋፋት ምክንያት በመኾን፤ ራሷም ኾነች ሀገር የቆሙበትን ትዳር ተቋሙን እያፈረሰች እንድትፈርስ አስተዋጽኦ ታደርጋለች።

(እንደመጣልኝ የምነግርሽ አይደለም ብዙዎች ስነግራቸው ጆሮ ዳባ ልበስ ያሉት በማስረጃና በመረጃ በተደገፈ ጥናት እንጂ)

ክርስትያኑ ማኅበረሰብ እንደ ማኅበረሰብ ከመቀጠል ይልቅ፤ በዝቶና ተባዝቶ ወንጌል-የምሥራቹን በማስፋፋት ጽድቅና ፍትሕ ከማስፈን ይልቅ፤ ራሱን በራሱ፣ ዘሩን በፈቃዱና በምርጫው ማክሰሙን መርጦ በዚሁ መንገድ ላይ እየተቻኮለ ይገኛል።

የሚያሳዝነውና የሚያስገርመው ግን ለዚሁ የራሳቸው ግዴለሽነት፣ ወኔ-ቢስነትና አሰስነት ጣታቸውን ሌላው ላይ መጠቆማቸው እንጂ፦ ኢኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ ግሎባላዜሽን...።

በእርግጥ እነርሱ ይህንን ጩኸት መስማት የማይፈልጉ ብዙዎች ምክንያታቸው የጥፋቱን ተጠያቂነት ከራሳቸው ስለማይወርድ፣ እርሱንም ስለማይቀበሉት ነው።

ቀናውን ሊያስተምሩት የሚገባቸው መምህራን፣ ምሁራን፣ ሊቃውንት የጥፋት መንገዱን በማሳለጥ(አሁን አሁን በመጣ የትዳር፣ የቤተሰብና የሥርዓተ-ጾታ ሥልጠና) ትውልዱ ከድጥ ወደ ማጥ የሚገባበትን የጥፋት ትምህርት ከዐለም እየቀዱ፣ እየበጠበጡና እያፈሉ በመስጠት ይግቱታል!

ታናሼ! በየትኛውም አጋጣሚና ምክንያት ውስጥ ብታልፊ ግን የትኛውንም ዓይነት ምክር "እወድሻለሁ፣ አውቃለሁም" ከሚልሽ መካሪም ኾነ ለፍላፊ ብትሰሚ፦ ፍቺም ኾነ ዲቃላ መጎተት ግን ውርደት፣ ላመጣሻቸውም ልጆች ጭንቀትና ኃፍረት ቢኾን እንጂ ጀብድ ጀግንነት አይደለም! አይኾንምም!

"ያላባት ልጆቿን የምታሳድግ፣ የተማረች፣ የተመራመረች፣ የተሾመች፣ በቤትም በውጪም የምትሠራ፣ ዘበናይ፣ ስኬታማ፣ ዕንቁ፣ ንቁ፣ ብቁ፣ ጠንካሪት፣ ታታሪት፣ ብርቲት፣ ጀግኒት፣ ተርቢት፣ ንቢት፣ አንበሲት፣ ...ሴት እናት፣ አያት..." እያሉ እያቆለጳጰሱ ሲነግዱብሽ እውነት አይምሰልሽ!

በተለይም ደግሞ እንዲህ ያለ ውዳሴ የሚያበዙ፣ ምስጋና የሚያግተለትሉ፣ ማቆለጳጰስም የሚወዱ ወንዶች ከሰውነት ልክ፣ ከወንድነት ቁና፣ ከአባወራነት ልዕልና የጎደሉ መኾናቸውን ጠርጥረሽ ተጠንቀቂያቸው!

ይህ ከንቱ ወዳሴ ላንችም ኾነ በተለይና ይበልጡንም ለልጆችሽና ለትውልድ ፍጹም አጥፊ፣ መጪ ሕይወታቸውንም አመሰቃቃይ፣ ጠላትም እንዲጋልባቸው የሚያመቻች ሸፍጥ ነውና አስተውይ!

ፍቺ፣ ዲቃላ መጎተትም ኾነ ሽርሙጥና ጀግንነት ኾኖ በየመገናኛ ብዙኃኑ "አንቱ" የተባሉቱ ሁሉ ሲቀሉበት፤ ጀብድ ተብሎ ሲነገርለት ስታይ ራስሽንም ኾነ ልጆችሽን ከዚህ ክፉ መንፈስ ለማራቅ ጸልዪ፣ ታጠቂ፣ ተሰማሪም እንጂ ወደ መንገዳቸው አትመልከች!

መዝሙረኛው እንዲህ ይላል
ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ።

መዝ ፩፥፩

አሁን የመጣው በተለይም በቤተክርስተያናችን "መምህራችን፣ አባታችን፣ ሊቅና ሊቃውንት" በምንላቸው በኩል በገንዘብ ኃይል መጥቶ፣ በሆዳደሮች ከሌላ ቋንቋ ተመልሶ የተጫነው፣ በባለሥልጣናቱም እየተገፋ ያለው ትምህርት፤

ይህን (ፍቺን፣ ዲቃላ መጎተትና ሽርሙጥናን) እንዳንቺ ባሉ ውብ፣ ውድ፣ ትኁት እህቶቼ ዘንድ እንዲለመድ የሚያበረታታ መኾኑን ታውቂያለሽን?

አላገባሽ እንደኾነ ከአባትሽ(ከወንድምሽ)፤ አግብተሽም ከኾነ ከባልሽ ተጣበቂ፦ ጊዜው ከፍቷል! አፈቂቤ ክፉ መካሪ፣ ልክስክስ ስሜት አባራሪ፣ ምስኪን ለሆዱ አዳሪ፣ ፍግም ባይ ባፍጢም ተደፊ በዝቷልና!

መቼም እንድወድሽ ታውቂያለሽ!
እወድሻለሁናም እንዲህ አልኩሽ!
አባወራው ወንድምሽ!💪

አባወራ

29 Jan, 03:30


https://youtu.be/Nw2V4-uad6o?si=O2tQQnUjQ5L7ddqF

አባወራ

18 Jan, 04:54


https://youtu.be/IJtHv_ler4g?si=ZmX6WiBy26LMWScP

አባወራ

17 Jan, 03:32


መሥራት ባንችል ማገዝም ሥራ ነው!
======================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

"ምን እንሥራ?" በሚል በተደጋጋሚ ለሚላክልኝ ጥያቄ...

ዐለም ትውልድን ከተፈጥሮአዊ ነፃነቱ፣ ከተፈጠረለት ምክንያቱ ጎትታ በባርነት ለሞት ተላልፎ እንዲሰጥ የምትሠራው ሸፍጥ መጠነ ሰፊ ሲኾን ለዚህም ደግሞ ሀገራችንም ኾነች ልጆቿ መጋለጣቸው አይቀርም።

በተለይም በፍርሃት ተቀፍድዶ፣ ለባርነት ወዶና ፈቅዶ ያደረውን አስቀድሞ የሚከተለው ባፍጢም የተደፋው ሆዳደሩ ልሂቅ በከፍተኛ ኹኔታ የተደራጀና የተቀናጀ ጥቃትን በሰው ልጅ ላይ ያለርህራሄ ይፈጽማል።

የቀደሙት ብዙኃኑስ ፈርተው፣ የተማሩትን እውነት ተጠራጥረው፣ ከአስተዋይ ነፍሳቸው ይልቅ ስጋት ባሕርይው የኾነ ስጋዊ ስሜታቸው ገዝቷቸው ፈርተው አለጩ፤ ከማለጫቸውም የተነሳ ራሳቸውን ለሚሠለጥኑባቸው ጠላቶች አሳልፈው ሰጡ።

የኋለኞቹ ጥቂቶቹ ልሂቃን ግን እውነቱን ሲያውቁት፣ ክፉና ደጉን የእነርሱንም መንስዔና መጨረሻ ሲረዱት ነገር ግን ደጉን አባት፣ ፍትሐዊውን አምላክ፣ የእውነቱንም አባት፦ ኃይሉን ክደው ከክፋት አብረው፤ ለእውነትና ለእውቀት ሕጻናት የኾኑትን በአስመሳይና ሸንጋይ ምላሳቸው ያስታሉ።

ልብአድርጉ! ይህንን ማሰናከያ የሚያስቀምጡ መሃይማን አይደሉም። ይልቁንስ "አዋቂዎች"፣ አውቀው በተገኙበት እውቀትና ኃላፊነት ከትውልዱ ድኅነት ይልቅ ሆዳቸውን (ጥቅማቸውን) አስቀድመው አሳሳች አሰናካይ እንቅፋት የሚጥሉ ሊቃውንት (ልሂቃን) እንጂ።

ቃሉም እንዲህ ይላል፦

በእኔም ከሚያምኑ ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን የሚያሰናክል ሁሉ፥ የወፍጮ ድንጋይ በአንገቱ ታስሮ ወደ ጥልቅ ባሕር መስጠም ይሻለው ነበር።

ማቴ ፲፰፥፮

የኾነው ኾኖ አንዳንዶች ምናልባትም ይህንን የጠላትና የሆዳደሮችን ሴራ ፈርቶና ሸሽቶ መቀመጥ ከጥፋት ሥራቸው እንደማያድን፤ እንደውም ከእርሱ መተባበር መኾኑን ተረድተው፦ ምን እናድርግ ብለው ይጠይቃሉ።

በትዳራችን፣ በልጆቻችን፣ በማኅበረሰባችን፣ በቤተክርስትያናችን፣ በሀገራችን ጉዳይ ላይ ከጠላት የሚሰነዘረውን ፍላጻ ለማስቀረት ባንችል ለመመከት፣ ለመቋቋም ምን እናድርግ?

ተገቢ ጥያቄ ነው!
አሁን ያለንበት ጊዜና ዘመን ከጠላትና ከግብርአበሮቹ ሆዳደሮች ስምሪት፣ ፈርተው ተደፍተው ከሚኖሩ ብዙኃኑም አንጻር ራሳችንንም ኾነ ልጆቻችንን ሊመጣ ካለው መከራ ለመታደግ አንዳች ፍሬ ያለው ሥራ ላይ መሠማራት ግድ ይለናል!

እንዲህም ተብሏል፦

ብዙ ሕዝብም ባየ ጊዜ፥ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች ተጨንቀው ተጥለውም ነበርና አዘነላቸው። በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱን፦ መከሩስ ብዙ ነው፥ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው፤ እንግዲህ የመከሩን ጌታ ወደ መከሩ ሠራተኞች እንዲልክ ለምኑት አላቸው።

ማቴ ፱፥፴፮-፴፰

በእርግጥ "ምን እናድርግ?" ብለው የጠየቁ ሁሉ ቅን አሳቢዎች ናቸው ብላችሁ እንዳትታለሉ። እኔንም ከአንዴም ሁለት ሦስቴ ከማልጠብቃቸው ትልልቅ ሰዎች በዚሁ ቅንነት ተጎድቻለሁና።

☀️ አንዳንዶች እንዳው ደርሰው "ቅን አሳቢ" ለመባልና በስሙ ለመነገድ እንዲህ ማለት ብቻ ሳይኾን ተቋም እስከ መክፈት ይደርሳሉና።

☀️ አንዳንዶች ደግሞ "ምን እናድርግ" ብለው ከሚሰበሰቡ ሰዎች ጥቅም ለማግኘት፣ እንዲደረግላቸው ፈልገው ከተሰበሰቡ እግዚአብሄርን ተስፋ ባደረጉ ልጆቹ ለመንገድ ይጠይቃሉና።

☀️ አንዳንዶች ደግሞ ከጠላት ጋር የተሻረኩ ምንደኞች ሲኾኑ የቀጣሪያቸውን ጠላት ክፉ ሥራ በመልካም የሚያከሽፉትን ሰዎች ለማወቅ፣ ለማቅረብ፣ ለማጨናገፍ እንዲህ ይጠይቃሉና።

☀️ አንዳንዶች ግን እንዳው ከልክ ካለፈ ነገር ግን በሥርዓትና በዓላማ ካልተገራ ግዳጅንም ከማይፈጽም ጭንቀትና ብሶት የተነሳ ጠይቀው ለሆዳደሮቹ ሲሳይ በመኾን የሚያርፉ ይኾናሉ።

☀️ ጥቂቶች ብቻ "ምን እናድርግ?" ብለው ጠይቀው፣ ችግሮችን ነቅሰው ለይተው፣ እነርሱንም ዘርዝረው ተረድተው፤ ከቻሉ መፍትሔ ጠቁመው፣ ራሳቸው ቀድመው አለበለዚያ ደግሞ የእነርሱ እስኪገለጥላቸው መፍትሔው ከታየው ደርሰው ለማገዝ የሚተባበሩ ናቸው።

እንግዲህ ከወዴት እንደወደቅክ አስተውል!

ወንድሞቼ! ብዙ የሚሠራ ሥራ አለ! እውነቴን ነው የምላችሁ ደክሞኝ፣ ርቦኝ፣ ዐይኔም ቦዞ ራሴንም ስቼ እስክተኛ ድረስ በጣም ብዙ ሥራ አለ።

እውነት ሥራ ፈታችሁ ቲክቶክና ቲቪ፣ ኳስና እንቶፈንቶስ ላይ የምታጠፉት ጊዜ አላችሁን? እውነት እላችኋለሁ ለጊዜው የምትሠሩት ግር ቢላችሁ፣ ከየት መጀመር እንዳለባችሁ ቢቸግራችሁ እንኳ ሥራ ያላቸውን፣ ሥራ የበዛባቸውን ማገዝም ሥራ ነው!

ልብ አድርጉ! መከተል አላልኩም ማገዝ እንጂ!

አንዳንዶች "እንቶኔ ጥሩ ሥራ ይሠራል በዩቲዩብ ላይ፣ በቴሌግራም ላይ፣ በቲክቶክ አልያም በመጽሐፍ ስከተለው ስንት ዓመት ኾነኝ መሰለህ!"

ይህ ተገቢ አይደለም! መኸሩ በበዛባት ዐለም ተከታይና ተመልካች መኾን ሳይኾን ተሳታፊና አጋዥ መኾን ብቻ ነው ፍሬ የሚያፈራ፣ ያፈራውን የሚሰበስብ፣ እርሱንም ከጎተራ የሚከት።

የምትሠሩ ሰዎችም በተቻላችሁ መጠን ሸፍጠኛዋ ዐለም በምትሠራበት መንገድ "ተከተሉኝ፣ ተከታተሉኝ፣ አጋሩልኝ፣ ተከታይ አብዙልኝ፣ እንብዛ፣ ድምጻችን ይሰማ" ማለታችሁን ትታችሁ ተሳታፊና አጋዥ፣ ሠራተኛም ትውልድን አፍሩ!

ሲኾን የተፈጠረለትን ዓላማ ዐውቆ፣ የሚኖርበትን ምክንያቱን ጠንቅቆ ወደ እርሱ በእውነት ለጽድቅና ለፍትሕ የሚፋጠንን ትውልድን ሥሩ!

ባይኾን ደግሞ ከእናንተ በሰማው እውነት ታንጾ የሚኖርለት ምክንያቱ የጠራለትን፣ የተጠራለት ዓላማ የለየለትን የሚያግዙ ሠራተኞችን ሥሩ!

በእነዚህ መካከል የሰፈሩት "ተከታይ ብቻ ነን" ቢሉ ፈርተው ከሚረገጡት አልጮች ትንሽ ከፍ ብለው የሚሰየሙ ምስኪናን ኾነው አድማቂና አጨብጫቢ፤

አልያም ደግሞ የሚኖሩለት ዓላማ ያላወቁ፣ ለማወቅም የማይጥሩ ሰነፎች ነገር ግን ለዓላማው ራሱን መስዋዕት አድርጎ በሚሮጠው ላይ የሚበሳጩ፣ በሰመረለት መስዋዕቱም ፊታቸው የሚጠቁረውን ቃየናውያንን ማትረፋችሁ አይቀርም።

ስለኾነም የምትሠሩ ተከታይ ለማፍራት አትድከሙ! ከተከታይ ይልቅ አጋዥ ሠራተኛ የኾኑ ይህንንም ከጽድቅ የሚቆጥሩትን አትርፉ።

ለጊዜው የምትሠሩት ግር ያላችሁ ነገር ግን በሚሠራው ጽድቅ ያመናችሁ ደግሞ ተከታይ፣ አድማቂ፣ አጨብጫቢ ከመኾን ይልቅ ተሳታፊ አጋዥም በመኾን ከጽድቁ ተካፈሉ!

እንደምታውቁት ለአባወራ ገጻችን ከአንድ ሺህ ስድስት መቶ በላይ ተከታዮች ብዙ ናቸው ብቻ አይደለም፤ እጅግ በጣም ብዙ በርካታም ናቸው እንጂ!

ጽድቅን ለመሥራት እልፍ አእላፍትን ሳይኾን ጥቂት እውነትን ይዘው በራሳቸው ላይ የጨከኑ ጽድቅና ፍትሕን ለመሥራት ራሳቸውን የሚሰዉ፣ አጨብጫቢ ተመልካች አድማቂ የማይፈልጉ ቆራጦች እንደሚያስፈልጉ አስተውሉ!

ተከታይ ሳይኾን ቀድሞ የሚሠራ(የሚያወራ የሚጮህ አይደለም) ባይኾን ግን በማገዝ የሚሳተፍ ትውልድ ማፍራት እንጂ ተከታይ ማስከተል የገጻችን ዓላማ አይደለም።

ስለኾነም ማወቅ ቀዳሚው ኾኖ ባወቅነው ልክ ለመሥራትም ኾነ ለማገዝ ደግም ተመሳሳይ ዓላማ ካላቸው ጋር ሕብረት አንድነት መፍጠር ተገቢ ነው!

በዚህ አጋጣሚ ማገዝ ማለት ማውራት፣ ወሬንም የገቢ ምንጭ ማድረግ ለማለት አይደለም! "ብዬ ነበር፣ ስንት ዓመት ተናግሬ ሰሚ አጥቼ ነው፣ ይህንንም ያንንም አስጠንቅቄ ጮኬያለሁ" ማለትም መሬት ላይ ለውጥ አያመጣም!

አባወራ

15 Jan, 15:05


የቻሉትን ደልለው፣ ምን ቢማሩ ሊቅና ሊቃውንት ቢባሉ በሆዳቸው ባፍጢማቸው የተደፉትን በገንዘብ ገዝተው፣ በሊቃውንቱ የሚደገፉ ዐዳዲስ ትርጓሜን በያዙ ንቅናቄዎች ትውልዱን አታለው የጥንካሬው መሠረት፣ የቤተክርስትያኗ ገንቢ የኾነ ቤተሰቡን ለማፍረስ በተለይም ወንዱን ለመስለብ እንጂ!

ወደ ምናቤ፦ ተሜዎቹ ብዙ ጥያቄ አላቸው፦ ወንድ ማለትስ፣ ሴትስ፣ ባልስ፣ ሚስትስ፣ ወሲብስ... የየኔታን መልስ የምናየው ይኾናል።

አባወራ

15 Jan, 15:05


ቤተሰብ ካልፈረሰ የጾታ ጥቃት እኩልነትም አይቆምምን
=======================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

"አይቆምም" የሚለውን ቃል በሁለት ትርጉሙ ተጠቅሜበታለሁ።
፩ኛ "ለጾታ ጥቃት"፦ አይቀርም አይቀርልንም ወይ በሚለው፣ ትርጉሙ እና
፪ኛው ላይ "ለእኩልነት" ሲኾን ደግሞ የጾታ እኩልነት ቆመ-ተቋቋመ፣ ጸደቀ፣ ጸና...

ከታች ያለው አንድ የቤተክርስትያናችን ሊቅ የእኔን የጃንደርባ ቃል ትርጓሜ ተንተርሰው "መጽሐፍ ቅዱስ አንብቦ የሚያውቅ አይመስልም" ሲሉ ሰጡት በተባለ አስተያየት ላይ ተንተርሼ፣ ከራሳቸው ቃላት ተውሼ ያስቀመጥኩት የራሴ ምናባዊ ትዝብት ነው።

ሊቁ ተማሪዎቻቸውን አስተምረው አብቅተው ከማረፊያቸው ተሰይመዋል። ከተማሪዎቻቸው መካከል አንድ ሁለቱ ሮጠው ይመጣሉ።

👉 "ምን አመጣችሁ?" ማለት ማ እርሳቸው
👉 "በአንድ ቃል ላይ ተከራክረን" በችኮላ ተማሪዎቻቸውም፤
👉 "ምን የሚሉት ቃል ነው፤ መቼም አታመጡት የለ?" ቀጠሉ ሊቁ
👉 "አንድ አውቃለሁ ባይ ቀጣፊ፣ ልንገራችሁ ባይ ለፍላፊ ሄኖክ ኃይለገብርኤል(እኔን) የሚሉት 'ጃንደርባ ማለት ቆለጡ የተቆረጠ ስልብ፤ አንድም ወኔው የከዳው ሐሞት የለሽ ወኔ ቢስ ነው' ቢለን ሮጠን መጣን?"

👉 "ዋ! እንዴት ያለው መሃይም፣ መጽሐፍም ገልጦ የማያውቅ በተለይም መጽሐፍ ቅዱስን ያላነበበ ጨዋ ኑሯል?
'ጌታችን ስለ መንግሥተ ሰማያት ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደርቦች አሉ' ማለቱን አልተመለከተም..."

የኔታ ሄኖክን(እኔን) ልክ ስላስገቡላቸው፤ ተማሪዎቹ ተደስተው ተመልሰዋል።

ዛሬም ግን ልክ እንደ "ጃንደርባ" ቃል ሁሉ ነባርና ቀላል የኾኑ ሌሎችም ቃላት ተማሪዎቹን የኔታ ጋር ሊያሮጣቸው ነው። እርሳቸው ግን በዚህ ባልተማረ፣ መሃይም ሄኖክ(እኔን) የቃላት ትርጓሜ ሳይበሳጩ፣ በደቀመዛሙርቱም ላይ ትዕግስታቸው ሳያልቅ አይቀርም።

ሮሚና እስትራቲ የተባለችው ሴታቆርቋዥ (feminist) የዛሬ አራት ዓመት ገደማ የድልድል ፕሮጀክትን ይዛ መምጣቷን፣ ግቧንም አሳክታ መመለሷን ከዚህ በፊት እንደተወያየንበት ይታወቃል።

ለማስታወስም ያክል ይህ ፕሮጀክት "የሴቶችን ጥቃት ለማስቆም ታልሞ የተዘረጋ ነው" ሲባል፤ በተለይም ኦርቶዶክሳዊ የሚበዛባቸው ክልሎች ይበልጡንም በአማራው ክልል ላይ ትኩረቱን አድርጎ፣ ወንዱ የሚሠለጥንበትን መጻሕፍትና አጋር ተቋማትን በማፍራትና በማስታጠቅ ተጠናቋል።

ከዚህች ሴትዮ ጀርባ ያሉት ሁሉም ተቋማት ደግሞ ከዚህ በፊት ከዘረዘርኳቸው ዓላማዎቻቸውና አቋሞቻቸው በተጨማሪ ቤተሰብ የሚባለው ነባር ማኅበራዊ ተቋም ማፍረስ የሚፈልጉ ለዚህም ዓላማቸው ደግሞ የቤተሰብን ትርጉም የሚቀይሩ ናቸው።

እዚህ ጋር ከሰይጣን ተሻርኮ ለትውልዱ ጥፋት የተደረሰውን የካርል ማርክስን ዘመን ተሻጋሪ፣ ነቀርሳና መሰሪ ቃል አስታውሱ፦ ያለና የነበረ ሁሉ ሊጠፋ(ሊፈርስ) ይገባዋል፤ (Everything that exist shall perish)።

የሮሚና እስትራቲ ቀጣሪዎች፣ የላኳት ተኩላዎችም ቃላቸው ይህንኑ የካርል ማርክስን ነቀርሳ በጊዜውና በወቅቱ፣ ለጊዜውና ለወቅቱ እንዲኾን አድርገው ትውልዱን የሚያልጩ ናቸው።

እነዚሁ የአምልኮ መልክ ያላቸው ቃሉን የካዱ ክርስትያን ነን ባዮች ልሂቃን፤ እነርሱ የሚገልጹትን የቤተሰብን አላስፈላጊነት ለፍላጎታቸው ካለቦታው አምጥተው በለጠፉት የመጽሐፍ ቃል (ልክ እንደ የኔታ) ያጠናክራሉ።

እነዚህ አካላትም ኾኑ ግለሰቦች በባልና ሚስት ወይንም በእናትና አባት ይመሠረታል፣ ልጆች ይወለዱበታል፣ ዘመድ አዝማድ ይሰበሰብበታል የሚባለው ቤተሰብ በአንባገነኑ ወንዳዊ፣ አባታዊ፣ አባወራዊ(patriarchal) ሥርዓት የተበየነ ነው ይላሉ።

ስለኾነም "በባልና ሚስት ወይንም በአባትና እናት የሚመሠረት ቤተሰብ ተፈጥሮአዊ፣ ሕጋዊ፣ መጽሐፋዊ፣ አይደለም" ብለው ይሞግታሉ።

እነዚሁ ሮሚና ኢስትራቲን "ጎሽ፣ አበጀሽ፣ ምን ደረስሽ" እያሉ የሚያበረታቷት "የሃይማኖት ልሂቃን" ለዚህም ማስረጃ ሲያቀርቡ "እመቤታችን በሦስት ዓመቷ እናትና አባቷ ወደ ቤተመቅደስ ሲወስዷት የባህላዊውን ቤተሰብ መፍረስ፣ አለማስፈለግና ከቤተክርስትያን ትውፊት መለየት ያስረዳል...." ይላሉ።

ታዲያ እነዚሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያንን(ተቋሟንም ኾነ ማኅበረ ምዕመኑን) እንድታፈርስ በከፍተኛ በጀት ታጅባ እንደተላከችው መልዕክተኛዋ ሮሚና ኢስተራቲ ሴታቆርቋዦች (feminists) የኾኑ ግለሰቦችና ተቋማት ቤተሰብ ካልፈረሰ የጾታ ጥቃት አይቆምም፤ የሴቶችም እኩልነት አይሳካም የሚሉት የጋራ መፈክር አላቸው።

ስለዚህም የምናውቀውን፣ የምንግባባበትን፣ የምንዋደድበትንና የምናይልበትን(ኃይለኛ የምንኾንበትን) ቋንቋ ያንሻፍፋሉ።

ለዚህም ደግሞ በጥቅም የገዟቸውን ልሂቃን በማስቀደም እንደ እኔ ያልተማረውን ንግግሩ ጎልዳፋ፣ ጽሑፉ ሸፋፋ የኾነ መሃይም ጨዋም ዝም ያሰኛሉ።

ቤተሰብ ማለት በወንድና በሴት ወይንም በአባትና በልጆች ተመሥርቶ፣ በልጆችና በዘመድ አዝማድ የሚከበር ጥንታዊ፣ መሠረታዊ ሕብረት፣ አንድነት ነው አልኩኝ።

ምናባዊ ጨዋታዬ ጋር ልመለስ፦
👉 ተማሪዎቹ ዛሬም እንደ ከዚህ በፊቱ በሚያውቁት ቃል ተወዛግበው ኖሯል። ያው ከሄኖክ(እኔ) ሌላ ማን ያወዛግባቸዋል፤
👉 ሲሮጡ መምጣት
👉 ማን ጋር?
👉 የኔታ ጋር
👉 ሊቁም ጠየቁ "ምን አቻኩሎ አመጣችሁ?
👉 ቤተሰብ ማለት አባትና እና የሚመሠርቱት....ተቀባብለውና ተቆጥተው መጠየቅ?
👉 ማነው እንዲህ ያላችሁ? ፈጠን ብለው ሊቁ
👉 ይሄ ሄኖክ(እኔን) የሚባል ጸሐፊ? አንዱ ተሜ
👉 ኧረ ወዲያ ሂድልኝ! ጸሐፊስ አትበለው፤ አላዋቂ ለቅላቂ እንጂ
👉 ምን ይሻለኛል አሁንስ ይሄ መጽሐፍ ገልጦ የማያውቅ፣ መጽሐፍ ቅዱስ አንብቦ የማይረዳ፣ የቤተክርስትያንንም ታሪክ ያለተማረ ማይም፤ አንድ መቶ ሀያ ቤተሰብ የሚባሉት የአንድ አባትና እናት ልጆች ነበሩን? ኮስተር ብለው እናንተስ ይህን አታውቁም በሚል አስተያየት መለሱ
👉 ኧረ! እርሱ ብቻ አይደለም! ወንድምና እህት ማለት ከአንድ አባትና እናት የተወለዱ... እያለ...፤ አንዱ ተሜ አስከተለ
👉 እስከ መቼ ዝም ይባላል፤ እነሆ በመጽሐፍ ላይ፦

ገናም ለሕዝቡ ሲናገር፥ እነሆ፥ እናቱና ወንድሞቹ ሊነጋገሩት ፈልገው በውጭ ቆመው ነበር።
አንዱም፦ እነሆ፥ እናትህና ወንድሞችህ ሊነጋገሩህ ፈልገው በውጭ ቆመዋል አለው።
እርሱ ግን ለነገረው መልሶ፦ እናቴ ማን ናት? ወንድሞቼስ እነማን ናቸው? አለው።
እጁንም ወደ ደቀ መዛሙርቱ ዘርግቶ፦ እነሆ እናቴና ወንድሞቼ፤
በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነውና አለ።

መባሉን አያውቅምን። አሉ የኔታ፣ ሊቁ፣ ሊቀ-ሊቃውንቱ።

ወንድምዓለም! ጃንደርባ የሚለውን ቃል ትርጉም ለመረዳት መጽሐፍ ማገላበጥ አይጠበቅብንም ነበር ነገር ግን ጠላት በትውልዱ መካከል ያስገባው ነቀርሳ አጠራጠረን።

ይህ በዚህ አያበቃም ከላይ እንዳስቀመጥኩልህ ቤተሰብን የማፍረስ ዓላማ ያላቸው ግለሰቦችና አካላት፣ ስለ ቤተሰብ የሚፈልጉትን ትርክት የሚጎትቱ እነርሱ ሮሚና ኢስተራቲን ሲልኳት ሴት በዳይ፣ ሚስቱን ገዳይ ላለችው ኦርቶዶክሳዊ ብለው አስበውና ተጨንቀው እንዳይመስልህ።

አባወራ

15 Jan, 03:47


https://youtu.be/JfaNWbxJSSc?si=IW5e9VPGl6yqRll8

አባወራ

14 Jan, 15:00


ቤተክርስትያንን ከሚያዘጉት ሆዳደሮች ስንማር
=============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ይህ በምስሉ ላይ የምታዩት ቤተክርስትያን፦ በእንግሊዝ ሀገር፣ በካምቢሪጅሻየር ክልል፣ በፒተርብሮ ክፍለከተማ በካቴድራል ከተማ የሚገኝ ጥንታዊ፣ ታሪካዊ ቤተክርስተያን ነው።

ይህ ቤተክርስተያን እንደ ኤውሮፖውያን አቆጣጠር በ650 ዓመተ ምህረት አካባቢ እንደተመሠረተ(በእኛ በ633 ዓ.ም. አካባቢ ማለት ነው) ከመረጃ መረብ ያገኘኋቸው የታሪክ መዛግብት ይጠቁማሉ።

ይህ ካቴድራል በተለያዩ ጊዜያት በቃጠሎም ኾነ በተለያዩ ምክንያቶች ለሚደርስበት ጉዳት እድሳት እየተደረገለት አሁን የምታዩትን እጅግ ማራኪ መልክ ይዞ ቆይቷል።

ይህ ካቴድራል በእንግሊዝ ካሉት ሁሉ እጅግ አስደናቂ የኾነ ኪነ-ሕንጻ እና እድሜ ያለው ሲኾን በዚህም በርካታ ጎብኚና ዝና አትርፏል።

ላለፉት አንድ ሺህ ሦስት መቶ ሰባ አራት ዓመታት በአካባቢው ላሉትም ኾነ ከተለያዩ አካባቢዎች ለሚመጡ ክርስትያኖች አገልግሎት ሲሰጥ የቆየው ይህ ጥንታዊና ታሪካዊ ቤተክርስትያን ግን አሁን ከፍተኛ አደጋ ተጋርጦበታል።

እርሱም ለአገልግሎት ክፍት ኾኖ ለመቆየት የሚያስፈልገውን ወጪ መሸፈን የሚያስችሉት የምዕመናን ማኅበር፣ ከእነርሱም የሚገኝ ገቢ በማጣቱ ነው።

የዚህ ገቢ ማጠር እና ቤተክርስተያኗን የመዘጋት አደጋ የጋረጠባት፤ በአካባቢው የሚኖር፣ ሊመጣ የሚችልም ክርስትያን ጠፍቶ አልነበረም። ነገር ግን እረኞቿ ማኅበረ-ምዕመኑን ከመያዝ፣ ወደ ጽድቅ በእውነት ከመምራት ይልቅ የዐለምን ተራና ተርታ ወሬ አጀንዳ አድርገው ትውልዱን የሚያደነቁርና የሚያርቅ መርሐግብር መዘርጋታቸው ነበር።

በተለይ የጾታ፣ የሥርዓተ-ጾታና የዐየር ንብረት ለውጥ ቤተክርስትያኗ ከተቆመችለትና ከተቋቋመችለት የወንጌሉ የምስራች ይልቅ በልሂቃኖቿ ቦታ ተስጥቶት ነበር።

እኛ የምንሰማው ትውልዱ ከቤተክርስትያን እንደቀረ፣ እየቀረም መምጣቱን እንጂ በምን ምክንያት፣ ለምን እና እንዴት ባለ የተቀነባበረ ሸፍጥ እንዳስቀሩት አይደለም።

በሌላ በተያያዘ ዜና ባለፉት አስር ዓመታት ውስጥ ብቻ በዚያው በዩናይትድ ኪንግደም ከሁለት ሺህ በአብያተ-ክርስትያናት በላይ በተለያዩ ምክንያቶች ተዘግተዋል።

ወንድምዓለም! ትናንት ዐለምን ቅኝ በመግዛትና በማቅናት ሰበብ ክርስትናን እስከ ዐለም ጥግ ያደረሰችና ያዳረሰች ጥንታዊት ሀገር፤ ዛሬ በራሷ ልሂቃኖች፣ በተለይም ባፍጢም በተደፉ ሆዳደር የቤተክህነት ሊቃውንት እየተሸጠች ነው።

ከዚህ እንማር!

ልብ አድርጉ! እንዲህ ለመፍረሷና ለመጥፋቷ ከፍተኛውን ሚና የተጫወቱት በቀዳሚነት፦
፩ኛ ይህ ሁሉ ሲኾን ዝም ብለው የኖሩ ብዙኃን እንግሊዛውያን አልጮች ሲኾኑ በቀጣይነት ደግሞ፣

፪ኛ የተጠሩለትን እረኝነት በምስር ወጥ የለወጡ ሆዳደር ጳጳሳት፣ በስተመጨረሻ ግን

፫ኛ እነዚያው ቤተክርስትያኗ እንድትጠፋ የሚፈልጉ በሀገርም ኾነ በውጪ የሚኖሩ ጠላቶች ናቸው።

ታናሼ! የአበራሽን ጠባሳ ያየ በእሳት አይጫወትም እንዲሉ፤ እነርሱ እንግሊዛውያኑ አጀንዳ አድርገው የወደቁበትን፦ ጠላት የዘረጋውን፣ ሆዳደሮች ያጸደቁትን፣ ምዕመኑ በዝምታ የተቀበለውን ይኸው ተመሳሳይ ሸፍጥ አንተም ጋር መጥቷል።

እውነትን ማወቅ፣ እውነትን መመስከር፣ ስስለ ፍትሕም መቆምና ስለ መሰከሩት እውነት መከራ መቀበል ሳይኾን "ጊዜው ምን አምጥቷል፣ ሰዉ ምን ይወዳል፣ ጥቆምና ዝና እንዴት ይገኛል፣ መንግሥት ምን ይፈልጋል" እና የመሳሰሉትን እያሰቡ መሰማራትና ማሰማራት ተንሰራፍቷል።

በዚህም ለቤተክርስትያኗም ኾነ ለሀገር መሠረቷ፣ መገንቢያ ጡብ ድርድራቷ የኾነውን ቤተሰብ የሚያፈርስ መርሐ-ግብር
🌟 በሥርዓተ ጾታ ስም፤
ከቆመችለትና ከተቋቋመችለት ዓላማ ጋር የማይገናዘብ አዘናጊ መርሐ-ግብር
🌟 በዐየር ንብረት ለውጥ (climate change) ስም አጀንዳ አድርጎ መፋጠን ተመርጧል።

በተለይ የቀደመው መርሐ-ግብር ቤተክርስትያኗን ከስር ከመሠረቷ የሚያፈርሳት ኹነኛ የጥፋት መንገድ መኾኑን ጠላት ያውቃልና፤ እርሱው ከመቼውም ጊዜ ይልቅ አጀንዳ ኾኖ በልሂቃኑ እየተገፋ ይገኛል።

ትውልዱ ለዘመናት ሲጠቀምባቸው፣ ሲግባባባቸው ሲስማማባቸውና ሲዋደድባቸው የነበሩትን ቃላት እነርሱ ምንዳ ለበሉበት አጀንዳ፣ ከፋያቸውን ደስ ለሚያሰኘው የጥፋት ሴራ እያጠጋጉ ትውልዱን ከተፈጥሮውና ከፈጣሪው መለየቱን መርጠዋል።

በሀገረ እንግሊዝም የኾነው እንዲሁ ነበር።
☀️ በሴቶች ተሳታፊነትና አሳታፊነት የጀመረው፣
☀️ ሴቶችን ወደ አመራር ማምጣት በሚል የቀጠለው፣
☀️ ግብረሰዶማውያንንና ሌሎችም "እግዚአብሄር በአምሳሉ የፈጠራቸውን" በማካተት የተቀጣጠለው፣
☀️ ሴቶችን ወደ ክህነትና ጵጵስና በማምጣት ያላቆመው፣
☀️ ግበረ-ሰዶማውያንንም ያስከተለው
☀️ ዛሬ ላይ እንዲህ ባዶ ያስቀራቸው መርሐ-ግብር ሲጀምራቸው ልክ አሁን እኛ ጋር እንደሚራገበው ነበር። በጭራሽ ግን እዚህ ደረጃ ላይ ይደርሳል ብሎ ያሰበው አልነበረም እንጂ!

ታናሼ! ይህንን ማን ጻፈው፣ ማንስ ነገረህ ቢሉህ፦ አንድ መጽሐፍ ገልጦ የማያውቅ መሃይም፣ ያለተማረ ጨዋ፣ የዲፕሎማ ሽፍታ፣ አንጋገሩሩ ጎልዳፋ፣ ጽሑፉ ሸፋፋ የኾነ ሄኖክ ኃይለገብርኤል ጽፎታል በላቸው፤ እነርሱ ሊቅና ሊቀ-ሊቃውንት ስለኾኑ!

ይህ ጽሑፍ ተራ ወሬ ብቻ አይደለም! እኔም "ሰሚ አጣሁ እንጂ ተናግሬያለሁ" ለማለት አልጻፍኩትም። እየሠራሁ፣ የምሠራውንና የማጠናውን ለታሪክም ኾነ ለእውቀት እየሰነድኩ እንጂ!

የቤተክርስትያን አደጋዋ የሚታያችሁና ከሆዳደርነት እርቃችሁ "ከየት እንጀምር?" ለምትሉ አለሁኝ፤ ባጠናሁት ልክ። ውድቀቷ ውድቀታችን ልማቷ ልማታችን ነውና! ለልጆቻችንስ ምን እናወርሳቸዋለንና!💪

አባወራ

13 Jan, 03:22


https://youtu.be/5nWarFJbpLU?si=Y_ljedXrO_t-SQTa

አባወራ

12 Jan, 04:09


https://youtu.be/5XIyxFiP3s8?si=K54u28AbpcCbrs6v

አባወራ

11 Jan, 02:53


ምንስኪን አልጫስ እንድንኾን ለምን ይፈለጋል?
=============================

https://youtu.be/FLbdw7OyvHI?si=9jqH0SQyj48yB1YM

አባወራ

10 Jan, 09:00


ዝምታን በመረጠ የእጃችሁ ፍሬ አታላዝኑ!
==========================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

"ስጦታችንን እንወቅ፣ ተፈጥሮአችንን እንጠብቅ፣ መክሊታችንን አንቅበር" ማለት፤ አባታችን አውቆ በሰጠን ጸጋ ሠልጥነን ጽድቅና ፍትሕ እንድንፈጽምበት ማሳሰቢያ ነው።

ማሳሰቢያው ዝም ብሎ የቃላት መደናቆር ብቻ አይደለም። ትውልድን ከሚያልጩ፣ ወኔውን ከሚሰልቡ ጠላትና የጠላት ቅጥረኛ-ምንደኞች ጋር በተግባራዊ ትምህርት የሚደረግ ትንቅንቅ እንጂ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን እውነቱን ስታውቁት፣ ከመጣው ጋር መዳራቱን(የሃሳብ መዳራትና መጋባት) ስትወዱት፣ ለሆዳችሁ አድልታችሁ በመረጣችሁት ዝምታችሁ ግን የሚኾንባችሁ ሁሉ የዝምታችሁ የእጃችሁ ፍሬ ነውና ስለ እርሱ አታላዝኑ!

እግዚአብሄር አምላካችን አባታችን የሞላ የተትረፈረፈ ጸጋን ሰጥቶ፣ ለዓላማችን መፈጸሚያ ለግዳጃችን መወጪያ በቂ መክሊትን አቅርቦ፤

ከእኛ በእውነት ላይ ቆሞ፣ ጽድቅንና ፍትሕን በመፈጸም ሠላሳ ስድሳና መቶ እንድናፈራ ሲጠበቅ ለሆዳችን አድልተን ባፍጢማችን ተደፍተን መከራን ብንሰበስብ አንደነቅ!

እርሱ ላይም አናላዝን! ፊታችንንም አናጥቁር!

በእውነት ላይ ቆመው በሚሠሩት ጽድቅ በሚያስጠብቁት ፍትሕ መከራን ቢቀበሉ፦ ልብ ያበራል፣ በጸጋ ላይ ጸጋን ይጨምራል እንጂ ፊትን አያጨማድድም፣ አንገት አያስቀልስም፣ ልብን አያሰብርም! ይህ አባታችን ያሳየን ፈለግ ነው!

በተሰጠን ጸጋ ሠልጥነን፣ በሠለጠንበት ጸጋ በልጽገን፣ ካበለጸግነው የእኛ ከኾነው ከእርሱ መርጠን በዐለም አደባባይ ስለጽድቅ የምነሰዋው፦ እኛን፣ የእኛ በኾነው ሁሉ ፊታችን ሊበራ እርግጥ ነው!

ነገር ግን አሁን ምን እየተነገረን እንደኾነ አስተውሉ! "ዋኖቻችን" ምን እያሳዩን እንደኾነ መርምሩ።

🌟 አውቀው ሊያስተምሩን፣
🌟 አስተምረው ሊያሠለጥኑን፣
🌟 አሠልጥነው ሊያበለጽጉን፣
🌟 በበለጸግንበት ጸጋችን(መክሊታችን) እውነትን ይዘን በዚህች ምድር እስካለን ድረስ ጽድቅን እንፈጽም ፍትሕን እናሰፍን ዘንድ ሊያሳዩን የሚገባቸው እነርሱ፤ ጸጋችንን እንድንጥል፣ መክሊታችንን እንድንቀብር ይመክሩናል።

ወንድምዓለም! የተሰጠህን ጥለህ፣ ተፈጥሮህን ቀብረህ በዝምታ በዘራኸው ዘር የቀጨጨ ምርት ብትሰበሰብ፣ የሳሳ ነዶ ብታጭድ፣ እንክርዳድም ማሳህን ቢወርብህ ፊትህ አይጥቆር፣ አትዘን፣ አታላዝንም!

እርሱ የእጅህ ፍሬ ነውና!

ምነው መልካም ስጦታን ሰጥቶህ፣ መርጦና ለይቶ መክሊት አስታቅፎህ፣ እርሱን አውቀህና ሠልጥነህበት ከተሰጠህም ይልቅ ሠላሳና ስድሳ መቶ ያማረ ፍሬ አፍርተህበት ልትበለጽግበት(ባለጸጋ ልትኾንበት) ሲገባህ የጣልከው፣ የቀበርከው አንተ፤

አንድም መልካም ስጦታን ሰጥቶህ፣ መርጦና ለይቶ መክሊት አስታቅፎህ ካገኘኸውና ከደረስክበት ማንነትህ (ስብዕናህ) መናኛውን መርጠህ የዘራኸው፣ የሰዋኸው አንተ!

ታዲያ ለምን በፍሬው፣ በውጤቱ ታዝናለህ! መልካሙን ብትዘራ፤ አንድም ከተሰጠህ ስጦታ፣ ከታቀፍከው መክሊት መርጠህ የሰባውን ብትሰዋ ፊትህ ይበራ አልነበረምን?

አንተ ግን የአውቃለሁ እብሪት ወጥሮህ፣ ሰጪውን ጌታ ተገዳድረህ፣ በወንድነት-መክሊቱ መሠልጠንና መበልጸጉን ትተህ፣ አልፎ ተርፎ ለኃጢያት ሰበብ ማምለጫ ስርቆሽ በር አድርገኸው፤ እርሱን መቅበርን ወደድክ፤ ይህንኑ የወደድከውን አሰስነትክን አጽድቀህም አስተማርክ!

እና ታዲያ ልታፈራበት ተሰጥቶህ ንቀህ በቀበርከው መክሊት-ወንድነትህ የተነሳ ብትገፋ፣ በትደፋ፦ "ተገፋሁ፣ ተደፋሁ" ብለህ ለምን ታላዝናለህ፣ ፊትህንስ ለምን ታጠቁራለህ?

በተሰጠህ ጸጋ፣ በታቀፍከው ወንድነት መክሊትህ ሠልጥነህና በልጽገህ እውነት ጨብጠህ፣ ጽድቅን ብትፈጽም ፍትሕን ብታሰፍን ፊትህ ይበራ አልነበረምን? ይህንን በማደድረጉ ሂደትስ የሚያገኝህ እሳት-መከራው የሚያጠራህ የሚያነጥርህ አልነበረምን?

ወንድምዓለም! አስመሳይነት፣ ሆዳደርነት፣ አጎብዳጅነት፣ ስለጊዜያዊ ጥቅም ሲባል የሚያውቁትን እውነት ክዶ መኖር በወንድነት ተፈጥሮ ውስጥ፣ ለግዳጅ ከታጠቅነው ጸጋ ከተሰጠንም መክሊት መካከል የለም!

ስለኾነም ከእውነት ርቀን፣ ዝምታን መርጠን በምንሰበስበው መራራ ፍሬ ፊታችን ሊጠቁር፣ ልናዝንና ልናላዝን አይገባም! እርሱ የእጃችን የሥራችን ውጤት ነውና! ዋጥ!

አባወራ

09 Jan, 17:04


የትውልዱን ሚና መለየት ያልቻሉ ይደባልቁ
=============================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

"ትውልዱን የወንድና የሴት ሚና የሚባል፣ ሥርዓተ ጾታ የሚባል፣ ወንድ ይህንና ያንን ይሥራ የሚባል ተፈጥሮአዊ ነገር የለም።

ይህንንስ ያመጣብን ለዘመናት ተጭኖን የነበረ፣ ሴቶችን ጨቁኖ የነበረ፣ ሕጻናትን ሲበድል የነበረው ወንዳዊው አባታዊው ሥርዓት ነው" የሚለውን ትምህርት ከቤተክርስትያን መምህራን መስማት እየተለመደ መምጣቱ ዐዲስ አይደለም።

ይህ ብያኔ እዚህ ላይ የሚቆም እንዳይመስላችሁ ነገ ወንድና ሴት የለም ወደሚለው ያሳድጉታል። መጀመሪያ ይህንን በእኩልነት በተለይ በተለይ ደግሞ የጾታዊ ጥቃትን ማስቀረት በሚል ስም እንድንለማመደው እንጂ።

ለጊዜው ግን የቀደመው አጀንዳ ተይዞለት መጽሐፍ ተደርሶለት፣ መርሐግብር ተነድፎለት፣ ሥልጠና ተቀርጾለት በዋናነት የሚሰጥ በባለድርሻ አካላትም በመገናኛ ብዙኃንም ሽፋን የሚሰጠው ነው።

ከትውልዱ በተለይም ከወንዱ መሪ ማውጣት ያቃታቸው የቤተክርስትያን መምህራን፤ ካገኙ በልተው ካጡ ተደፍተው ከሚኖሩበት አልጫ ሕይወት ተነስተው አድማቂና ተከታይ ባፈሩበት የመገናኛ ብዙኃን ሁሉ ለወንዱ ተለዋጭ ሚና ይዘው መጥተዋል።

ቤተክህነቱንም ኾነ ቤተመንግሥቱን ለረጅም ዓመታት በመሪ ድርቅ እንዲመቱ ያደረጋቸው ማኅበረሰቡ ከተሰጠው መክሊት እርሱም ወንድ ልጅ መካከል ሠላሳ ስድሳና መቶ ፍሬ አፍርቶበት የኃይማኖትም ኾነ የሕዝብ አስተዳደር መሪ የሚኾን ትውልድ ከማውጣት ይልቅ ወንዱን ወንድነቱን እንዲቀብር ይህንንም ጽድቅ አድርጎ እንዲቆጥር ማስተማራቸው ነው።

ዛሬ እንኳን ለሀገርና ለቤተክርስትያን ይቅርና ለቤተሰቡና ለሚስቱ እንኳ የአባወራነት ግዴታውን መወጣት የማያውቅ፣ ከዚህም የተነሳ የማይችል በውጤቱም ለፈተና የተዳረገ ትውልድ ተገኝቷል።

በመካከል ጥቂት ለመድኃኒት ቢገኝ እንኳ አልጮች አልጫነታቸውን ያጋልጥባቸዋልና፦ አንባገነን፣ ልቡ በወንጌል ያልረሰረሰ፣ ከፍቅር ያልደረሰ ተብሎ እንዲገለል ይኾናል።

መምህራን ዛሬ በግልጽ የወንዱ ሚና መሪነት መኾኑን ክደው፣ ለእርሱም ሊሰጠው ከሚገባው ጊዜ፣ እውቀት፣ ጉልበት፣ ትኩረት ይልቅ በእኩልነት አሳበው ወደ ሚስቱ ሚና ሲጎትቱት ስሑት በኾነ ትምህርታቸው ከወንድነቱ እየሰለቡት፣ ጃንደርባ እንዲኾን እያስገደዱት እንደኾነ ያውቃሉ፤ ይህንንም ሠልጥነውበታል!

"እንዴት?" ብትሏቸው ዛሬ በቁፋሮ የተገኘ፣ አባቶቻችን ሳይደርሱበት የተበደሉበት፣ የበደሉበትም ግኝት ላይ የደረሱ ይመስል፤ የማይጎትቱት ትርጓሜ፣ የማይጠቀሱት ኃይለ ቃል የለም።

ይህንን በተለይ ለገጠሩ ማኅበረሰብ እንደ ሥልጡን ተቆጥሮ ሁሉም በአካሄዱ ወደ እርሱ የሚተምበት ከተሜውን ከተፈጥሮው ማራቅ፤

በተለይም ወንዱን በጽድቅ ስም ማለጭ ከተቻለ፣ በመገናኛ ብዙኃንና በማኅበራዊ ትስስር ገጾች፣ በአደባባይ/ በአዳራሽ መርሐግብሮች ይህንኑ ማስተጋባትና በሃይማኖት አባቶች ትምህርት በማጠናከር ትውልዱን ማለጭ ከባድ አይኾንም።

ወንድምዓለም! እውነትን ነግረውን፣ እውነትን ሰብከውን፣ በዚያ እውነት አርነት እንወጣ ዘንድ ስለ እርሷ የሚገጥመንን የፈተና ጽዋ ልንጨልጣት እንዲገባ የሚያስተምሩን አባቶች ዛሬ ከመጣው ሁሉ ተመሳስሎና አስመስሎ ለመኖር፣ አልፎ ተርፍ ረብጣ ብርና ዝና ከሰጣቸው ተደራድረው ትውልድን ለመሸጥ፦ ካባ ሲደርቡ፣ ቅኔ ሲዘርፉ፣ የጠላትን ልክነቱን በሚሥጥር ሲገልጹ መገኘታቸው ውድቀታችንን ያከፋዋል።

ዛሬ እውነትን በአደባባይ የሚነግሩን ሊቃውንት፣ መምህራን፤ ነገር ግን ስለ እውነት፣ ስለ ጽድቅና ፍትሕ መከራ በመቀበል ፋና ወጊ የሚኾኑልን ያልተማሩ መሃይምናን መኾናቸው ብዙ የሚያስረዳን ነገር አለ።

ይህ በእንዲህ እያለ ታዲያ ወንዱ የቤቱ የሚስቱ ራስ እንደኾነ ከማስተማር፣ እንዲያ ኖሮም ከማሳየት ይልቅ ጥቅስና ታሪክ ምሳሌና ትርጓሜ እየተመዘዘ እኩልነትን መስበክ የጠላት ሸፍጥ እንዳለበት አስተውል።

በመገናኛ ብዙኃኑም ቢኾን የቤተክርስትያኗ ልጆች በሚያስተዳድሯቸው እንኳ ሳይቀር ወንዱ እንዴት ያለ ዶሮ አጣቢ፣ ወጠ ሠሪ፣ ዳይፐር ቀያሪ፣ ሚስቱን ተላላኪ፣ እንደኾነ ቢያስተሞሩ እንጂ ቆፍጠን፣ ፈጠን፣ ኮስተር ብሎ ራሱን ችሎ ቤቱን የሚመራውን አያሳዩንም።

እንደውም ከዚህ ከፍቶ ሰካራም፣ ሴሰኛ፣ ሱሰኛ፣ ሚስትና ልጆቹን ደብዳቢውን ወንድ እያቀረቡ ትውልዱ በተለይም ልጆች ወንድነትን አባትነትን እንዲጠሉ መሠረት እየጣሉ ነው።

ድራማዎችን፣ ማስታወቂያዎችን፣ ፊልሞችን ሁሉ እዩዋቸው እስቲ ወይ፦ የእኔ ውድ፣ ውዴዬዬዬ፣ አትወጂም እንዴዬዬዬ፣ እያለ የሚለፋደድ፣ ቀኝና ግራውን የማይለይ፣ ከልጆቹ የባሰ ልጅ የኾነባትን ባል ታያላችሁ፤

በእርሱ አንጻር ደግሞ ቆፍጠን፣ ፈርጠም ያለች ልጅ መውለድ ተፈጥሮዋ ኾኖ እንጂ ባትወልድ ሌላ ትልቅ ሕልም የነበራት፤ እርሱንም፦ ከቤቱ አስተዳደር፣ ከቤት ውስጥ ሥራ፣ ከልጆች ክብካቤ ከሁሉም የሚከፋው ደግሞ ከአርባ መቱ ሕጻን ባሏ ጋር አስማምታ ለማሳከት የምትደክም አንዲት፦ ጠንካራ፣ ዕንቁና ብቁ ሴት ይሰጣችኋል።

እነዚህ ሁሉ ትውልዱን የሚያልጩ(ወንዱን አልጫ ሴቷን አመጸኛ የሚያደርጉ) መርሐግብሮች የሚሠሩት በኦርቶዶክሳውያን ተዋንያን፣ ደራሲዎች፣ አዘጋጆች፣ ዳይሬክተሮች፣ የመገናኛ ብዙኃን ባለቤቶች ነው።

ግን ለምን?

ይህን አታስተውሉትም እንጂ ምናልባትም "የሚያስቅ" ነገር አግኝታችሁበት ገልፍጣችሁ ታልፉታላችሁ፤ ይኹንና የእናንተን በተለይም ደግሞ የልጆቻችሁን አእምሮ እያለጩላችሁ (brainwash and demoralize) እያደረጉዋቸው እንደኾነ አታስተውሉም።

ታናሼ! እነርሱ ራሳቸው በወንድነት ልኩ፣ እርሱ በሚሰፈርበት ቁና አልተገኙምና ከእርሱም ጎድለዋልና ለትውልዱ የሚሰጡት ያንኑ በጉድለት የተገኙበትን አልጫነት ነው።

እጅግ የሚከፋው ደግሞ ይህንኑ አልጫነት ትውልዱን ጽድቅ ነው ብለው ማስተማራቸው ዛሬ ቤተክርስትያንም ኾነች ሀገር ትውልዱም ጭምር እውነተኛ እረኛ እንዲራብ ምክንያት ኾነዋል።

ትውልዱ አባቱ የሰጠውን ሚና አውቆና ሠልጥኖበት በልጽጎበትም እንዲያይል አውነትን ይዞ ጽድቅና ፍትሕን እንዲፈጽምበት ባይችሉ መደባለቅ መደበላለቃቸው አለማወቅ ብቻ ሳይኾን የጠላትም እጅ ያለበት ነው።

አባወራ

09 Jan, 10:03


ያለጨ ትውልድ በመግባቢያው ግራ ይጋባል
=============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ሰሞኑን "ጀንደርባ" የሚለውን ቃል አንስቼ በጻፍኳቸው ጽሑፎች ስለ ቃሉ የምናውቀው፣ ለማወቅ የምንፈልገውና ነው ብለው የያዝነው ትርጉም ትውልዳችንን ለማለጭ የፈለጉ ሰዎች ምን ያክል ውጤታማ እንደኾኑ ያስረዳል።

በውስጥም በፊትለፊትም ከተሟገትኳቸው ጥቂቶች ውስጥ አብዛኞቹ ከቃሉ ይልቅ በቃሉ ስለተመሠረተው ማኅበረሰብና ስመሥራቹ ግለሰብ ጥብቅና ከመቆም የተነሳ የሚሞግቱ ናቸው።

መጨረሻቸውም እንደተለመደው፣ እንደምጠብቀው "አንተ በቃ ማኅበሩን አትወደውም፣ የጃንደርባውን ትውልድ ትጠላለህ፣ ትልቁ ጸብህ ከመሥራቹ ነው" ኾኖ ይጠናቀቃል።

ወንድሞቼ! እውቀት የባሕርይ ገንዘቡ የኾነ መድኃኔያለም ዐይነ ልቦናችሁን ያብራላችሁና እንደው ይልንን ቃል እንድትረዱት ከመጽሐፍት በምስል ቀድቼ አመጣሁላችሁ።

እነዚህን መጽሐፍ መካድ ትችላላችሁ ነገር ግን እነርሱን ውድቅ የሚያደርግ አሳማኝ ትንታኔ ማቅረብ ሳትችሉ "ምንም ይኹን ምን ግን ማኅበሩን እደግፋለሁ፣ መሥራቹንም እወዳለሁ" ማለት መጀመሪያውኑ በእውቀት ሳይኾን በስሜት እጅ ደመጣን ይገልጣል።

የትውልድ ማለጭ አልጫ መኾን፤ አልጫ በእ

አልጫ በእኛ ዐውድ(context) የያዘው ትርጉም፦
🚨 አልጫ(1)፦ coward, ፈሪ፣

🚨 አልጫ(2)፦
demoralized, ወኔው የተሰለበ፣ ሞራል ያጣ፣ ጽድቅን ለመሥራት መስዕዋትነት ለመክፈል(ቤዛ ለመኾን) ተነሳሽነት የጎደለው፤
ማንነቱን(ታሪኩን፣ ተፈጥሮውን) የጣለ(የካደ)፣ ግራገብ፣ ዐለም የሰጠችውን ሳይመረምር የሚቀበል፤
ጎስቋላ (በአካልም ኾነ በሥነ-ልቦና)፣ በስሜቱ በሰውነቱ ላይ መሠልጠን የተሳነው ድኩም፤
ባርነት የተስማማው፣ የሚስማማው ከዚህም የተነሳ ዕጣ ክፍሉ የኾነ፣ ወዶ-ገብ ባርያ።

ዛሬ ጃንደርባ ላይ እንዲህ በመጀመሪያው መግባቢያ ቋንቋችን ግራ ስንጋባ አትገረሙ ነገ ከዚህ ባነሱ ቀላል ቃላትም ጎራ ለይተን እንጣላለን።

እነዚያ "በሥልጣኔ ቀደሙን" የምንላቸው ሀገራት ዘንድ፤ የተማሩና የተመራመሩ ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች እንኳ ተጠይቀው ሊገልጡት፣ ሊያስረዱት፣ ሊያብራሩት ያልቻሉት ቃል ምን ነበር?

What is a WOMAN?

ሰው ሴት ማለት ምን ማለት እንደኾነ ማስረዳት፣ ወይንም መግባባት አልቻሉም። "ሴት" ለጊዜው መርማሪው ሴትን ይምረጥ እንጂ "ወንድ" በሚለውም ቃል አይግባቡም።

ቃሉ ከባድ ኾኖ አልነበረም እኮ ነገር ግን እንዲህ ያለው አለመግባባት ላይ እንዲደርሱ ከልጅነት ጀምሮ የተማሯቸው መንገድ ጠራጊ የተሳሳቱ እሳቤዎች ነበሩና ነው።

የሶሻሊስት በሽታ የካርል ማርክስ ነቀርሳ በትውልዱ ውስጥ ተሰራጭቶ ተፈጥሮውን እስኪክድ፣ በመግባቢያው ግራ እስኪጋባ ድረስ ምን ያክል እንደተሰራጨና ያደረበትን አካል እንዳለጨ ኹነኛ ማስረጃ ነው።

ነገ ይህ እኛም ጋር ይመጣል፤ መንገድ ጠረጋው በአመርቂ ኹኔታ በታማኝ ምንደኞች፣ ትውልዱ አስቀድሞ እንዲያመልካቸው በተደረጉ ተቋማትና ግለሰቦች እየተቀላጠፈ ይገኛል።

ያን መሰሉ ነቀርሳ ሲመጣ ግን ተሸካሚዎቹ(the vectors) አርቲስቶች፣ ፖለቲከኞች፣ ኳስ ተጫዋቾች፣ ግንበኞች፣ ወታደሮች፣ ገበሬዎች፣ ነጋዴዎች ናቸው ብላችሁ እንዳትጠብቁ።

ይልቁንስ "ጾታዊ ሚና፣ ሥርዓተ ጾታ(Gender, Gender Identity) ማኅበረሰብ ሠራሽ ፍርጃ ነው" ብለው እንደሚያስተምሩት መምህር የዩኒቨርሲቱ ያውም የሥነ-መለኮት ፕሮፌሰሮችና ዶክተሮች እንጂ።

ዛሬ ጃንደርባ ላይ እንዲህ ተወዛገብን ነገ ግን፦

🌟 ወንድ ፣
🌟 ሴት፣
🌟 ትዳር፣
🌟 አባት፣
🌟 እናት፣
🌟 ባል፣
🌟 ሚስት፣
🌟 ልጅ፣
🌟 ቤተሰብ፣
🌟 ቤተክርስትያንና
🌟 ሀገር የሚባሉትም ቀላልና መሠረታዊ ጥንታዊም ቃላት ላይ ከማግባባት ይልቅ የሚለያዩን ይኾናል።

እናንተ አታውቁ ይኾናል። በእርግጠኝነት ግን ጠላት በቅደም ተከተል፣ የፊተኛው ለኋለኛው መንገድ እንዲጠርግ፣ እንዲቀባበል፣ የኋለኛውም ከፊተኛው ተቀብሎ ከእርሱ ለከፋው ኋለኛ እንዲያቀብል ተሰናድቷል።

ያንጊዜ "አባት ማለት ወላጅ የልጅ አባት ነው ብል" የቱ ጋር፣ እስቲ አንድምታውን አምጣው፣ እዚህኛው ላይ ያልወለዱም አባት ተብለዋል፤ ለምን አባት ብለህ ሮጠህ ለወለደው ብቻ ትሰጠዋለህ።

ይህ ወላጅ አልባ ሕጻናትን በማደጎ ከሚያሳድጉ፣ ወንበር ዘርግተው በእወቀት ደቀመዛሙርት ከሚወልዱ... ጋር ጸብ እንዳለህ፣ እንደማትወዳቸውና ጥላቻህን እየገለጽክ እንደኾነ ያሳያል......"

ቤተሰብ ማለት አባትና እናት ልጆም ነው ብትሉ ማን አለህ ብቻወን ያላባት ልጆች የምታሳድገው ቤተሰብ የላትም እያልክ ነው? አባትና እናት ሞተውባቸው ተረዳድተው የሚያድጉ ልጆች ቤተሰብ የላቸውም ማለትህ ነው? ጥላቻህን እየነገርከን ነው?
.
.
.
ተዘጋጅቶልናል! ተዘጋጅተውልናልም ሁሉንም በወረፋ "ለእኛ አስበውና ተጨንቀው" ይግቱናል፤ እኛም ያለ ተቃውሞ "ተዉ" የሚለንን "አንተ ከመምህራችን ትበልጣለህ፣ ማኅበራችንን ትጠላለህ" እያልን በደስታ ወደ ባርነትና ሞቱ...

ከማንግባባበት ግራ ከምንጋባበት ተከፋፍለንም ለጠላት እራት የምንደርስበት ሸፍጥ እንዲህ ያለው ነው!

ከትውልዱ ግነ ማን አስተዋለ!

አሳዛኙ ነገር እንዲህ ባሉት "መምህራን" ያለጨው ማኅበረሰብ ልከኛውን፣ ዐለም አቀፉን፣ ተፈጥሮአዊውን እውነት (Universal, Objective Truth) ዐይኑን ብትቧጥጡት እንኳ ማየት አለመቻሉ አለመፍቀዱም ነው።

በዚህም ራሱን ብቻ ሳይኾን ልጆቹን፣ ትዳሩንና ቤተሰቡን ማኅበረሰቡንም ይዞ ወደ ማጥ መግባቱን ጀብድ አድርጎ መቁጠሩ ነው።

ወንድሞቼ! ብናስተውል ጥሩ ነው! ሳናውቀው፣ ሳናስተውለው ይህ ክፉ በሽታ በሕዋሶቻችን እየተሰራጨብን፣ እያለጭን፣ እያለጩንም ነው።

ነገ ይረፍዳል! የሥራ ዕለቱ ዛሬ፣ ሰዓቱም አሁን ነው! አልጫ ትውልድ አሳድገን በአፍ መፍቻ፣ በመግባቢያ ቋንቋችን መግባባት የሚቸግረን ግራ-ገቦች ሳንኾን በፊት እንፍጠን!

አባወራ

09 Jan, 08:55


የወንዱ መሪነት ከራሱ ከቤቱም ይጀምራል
=========================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

በአባወራ ሥልጠናችን ወንዱን ግድ ከምንለው ነገር አንዱ ራሱን በእውነት ወደ ጽድቅ እና ኢፍትሐዊ በኾነችው ዐለም ፍትሕ ፈጻሚ እንዲኾን ማብቃት፤ ሚስትና ልጆቹን እንዲሁ መምራት ነው።

ይህን ግዴታ ለመወጣት ግን ያለውን፣ የተሰጠውንና የሠራበትን ማወቅ፣ ሊሠለጥንበትም እንዲገባ መረዳት አለበት። ጸጋውን የረሳ መክሊቱን የቀበረ እርሱ ማንም የመሪነቱን ሚና መጠበቅ፣ ግዴታውን መወጣት፣ ኃላፊነቱንም መፈጸም አይችልም።

ትውልዳችን በተለይም ወንዱ ራሱንም ኾነ ቤቱን እንዲመራ ግድ ከማለት በፊት በተሰጠው ጸጋ፣ በተቀመጠለትም መክሊት መሠልጠንና መበልጸግ እንዳለበት አይማርም።

ይህንን ሊያስተምሩ ያላቸው ወላጆች በተለይም አባት፣ ሲቀጥልም ማኅበረሰቡና ቤተክርስትያን ይህን ኃላፊነታቸውን ዘንግተዋል።

በቤተክርስትያንም ኾነ ባለድርሻ አካላቱ (ማኅበራት) ራሱን መርቶ ሌሎችን ማስከተል የሚችል እረኛ ማውጣት አልተቻለም። የመሪ ድርቅ ከቤተክህነት እስከ ቤተመንግስት የመታን ከዚሁ ካላበቃነው ትውልድ የተነሳ ነው።

ከዚህ የባሰው ደግሞ በተለይ በቤተክርስትያን(እንደ ተቋም)፣ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት(ማኅበራት) እንዲሁም መምህራን ወንዱ ጭራሽ ይህ ከወንድነቱ የተገኘው ሚናው ማኅበረሰብ ሠራሽ ፍርጃ እንጂ ከአምላኩና ከአባቱ በመክሊቱ(logistics) ታጅቦ በተጠያቂነት የተሰጠው እንደኾነ መካዳቸው ነው።

ይህንንም ከአመንዝራዋ ዐለም የቃረሙትን ትምህርት በሥልጠና መመሪያ አዘጋጅተው ወንዱ የተሰጠውን ጸጋ እንዲጥል፣ እንዲጠላውና እንዲተወው ያስተምሩታል።

ሴቷን አባቷ እንዳሰበው በትኅትና ተገዝታለት እንድትራዳው ሳይኾን በእኩልነትና በመሪነት ሰበብ አመጸኛ እና ተፎካካሪው ያስተምሯታል።

ይህ ብቻ አይደለም። በዓላማ ይህንኑ ጉዳይ የሚደግፉ፣ የሚዪግዙና የሚያጠናክሩ መርሐግብሮችን አዘጋጅተው በስሜት የጋለውን ትውልድ ስሌቱን ትቶ ስሜቱ ብቻ እንዲቀጣጠልና ለዚህ የተመቸ እንዲኾን ያራግቡታል።

ወንድምዓለም! ቤተክርስትያን እውነትን ይዞ ጽድቅ የሚሠራ ብቻ አይደለም ፍትሕን መፈጸምና ማስፈጸም እንዲችል ትውልድን ታበቃ ነበር!

ነበር!

አሁን በመርሕ ደረጃ ወንዱ የሚስቱ፣ የትዳሩ፣ የቤቱ መሪ-ራስም እንዳልኾነ፣ ይህም ሚናው አባታዊው ማኅበረሰብ ሴቶችን ለመጨቆን የፈጠረው እንደኾነ የሚያስተምሩ "ታላላቅ" መምህራን መጥተዋል። (ድሮም ነበሩ አሁን ጠላት በገንዘብ ገዝቶ ገለጣቸው እንጂ)

ይህም መመሪያ ተጽፎለት አመጸኛ ሴቶችን፣ አልጫ ወንዶች ከእነርሱም የሚገኙ ለባርነት የተመቹ ልጆችን፣ መረን የወጣ ትውልድም እንዲኾን ሥራ ይሠራል።

በ2013 ዓ.ም. በዐዲስ አበባ ባለ አንድ አጥቢያ ረቡዕ ማታ ከሥራ ስንወጣ ስለትዳር የሚያስተምሩን መምህር ወንዱ ቀድሞ የነበረውን፦ መሪ ነኝ፣ ራስ ነኝ፤ ሴቷ እናት ናት፣ ከልጆቿ መቅረብ አለባት፤ የሚባለውን ያረጀ ያፈጀ ግንዛቤውን ጥሎ ወደ ማዕድ ቤትና ወደ ዳይፐር ቅየራ መግባት እንዳለበት ሲናገሩ ዛሬ ለተዘረጋው ሸፍጥ መንገድ እየጠረጉ መኾኑን በወቅቱ ማን አስተዋለ!

ዛሬ መመሪያ ኾኖ መምጣት ብቻ ሳይኾን ከዚህ በተቃራኒው ማሰብና ማስፈጸም ጾታዊ ጥቃት ነው ብላ ራሷ ቤተክርስትያን ወንዶቿን ለመስለብ ከውጪ በእርዳታ ሰበብ በሚጋለቡ ሆዳደር መምህራን አማካኝነት ታስተምራለች።

በዚህ ብቻ አያቆምም! እንቢ ያለውን ወንድ ለዚህ በሠለጠኑና በተዘጋጁ ካህናት አማካኝነት ተገስጾ በአቋሙ ከጸና ከሰበካ ጉባኤ አባልነት ለመሰረዝ እንዲሰረዝም ታስቧል።

ጀግኖች! ደጋግሜ የምጽፍላችሁ በአባወራ ሥልጠናችን የወንዱ ተፈጥሮአዊ ጸጋ፣ አውቆ ሊሠለጥንባቸው የሚገባቸው ባሕሪዎቹ ውስጥ ድፍረት፣ ጥንካሬውና ሥልጣኔው ለራስነቱ አሰገዳጅ ግብዓት ናቸው።

ፈሪ አልጫም ወንድ፣ ስልባቦት የኾነ ጎስቋላ ወንድ፣ ጠባዩን ያላወቀ ያልሠለጠነበት መረንም የወጣበት ወንድ አይደለም ሚስቱንና ቤቱን ራሱንም መምራት አይችልም።

በድፍረትና ጥንካሬው ሥልጣኔውም የተሠራው ግን ይህ የድካሙ ፍሬ ከራሱ አልፎ ለልጆችና ለትውልድ እንዲተርፍ እንዲሻገርም ይህንኑ የምታከብርለትን ሴት መምረጥ አለበት።

አሁን እንደምናየው ማኅበራቱና የተለያዩ ተቋማት አመጸኛ ሴቶችን አልጫ ወንዶችን እያፈሩ የኦርቶዶክሳውያኑ ትዳርን ከድጥ ወደ ማጥ የሚያወርዱት እንዲሁ በአጋጣሚ አይደለም ኾን ተብሎ፣ ታቅዶና ታስቦበት የሚሠራ ነው።

አንተ በወንድነትህ፣ በተሰጠህ ጸጋ፣ በተቀመጠልህም መክሊት ሚስትህን፣ ልጆችህን፣ ቤትህን መምራት ካልቻል ምንም መምራት አትችልም።

መምራት አለመቻል ብቻ ሳይኾን ኑሮህም ከተፈጠርክለት መለኮታዊ ጥሪና ከተሰጠህ ጸጋ ጋር አይገናዘብምና አያሳርፍህም።

ይህም እንዲኾን ታዲያ ወንዱ ራሱን ችሎ መምራትና በዚህም ለሚስቱና ለልጆቹ እንዲተርፍ አለማሠልጠናቸው ሳያንስ ሴቷን በእርሱ ላይ በእኩልነት ሰበብ አመጸኛ አድረገው ያወጧታል።

"ሚስትህ ንብ ናት ማሯን ከፈለግክ ንድፊያዋን ታገስ አለዚያ ቁሻሻ ዘመዷ ጉዳፋ ወዳጇ ከኾነ ዝንብ ጋር ተጋባ" እያሉ የራሳቸውን አልጫነት የሚስታቸውን ተናዳፊነት ዕውቀት አድርገው የሚያስተምሩ መምህራንን እናውቃለን!

የብዙ የት ይደርሳሉ የተባሉ ኦርቶዶክሳውያን ባለ ትዳሮች ከእውቀት እውቀት ሳይጎድላቸው፣ ከገንዘብ ገንዘብ ሳይቸግራቸው፣ ከኑሮ ኑሮ ሳይጎድልባቸው ተናዳፊ ንብ-ሚስት ማግባት ስለ ማሯ ሲሉ አልጫ ኾኖ መኖርንም ጽድቅ ነው ብለው ተሰልበው ቀሩ!

ስንት? አንተ ስንት ታውቃለህ?

እኔ አሁን ይህንን እየጻፍኩኝ ስንት በቅርብም በሩቅም የማውቃቸው መውለድ አቅቷቸው መሐን ኾነው የቀሩ፣ አንድና ሁለት ልጅ ማሳደግ ከብዷቸው የሚያላዝኑ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊውን የትዳር-ተቋሙን ሥርዓት(hierarchy) ገልብጠው በአውቃለሁ እብሪት ተወጥረው "በእኩልነት" ማዕበል የሰመጡ ዐይኔ ላይ አሉ!

ወንድምዓለም! የአንተ መሪነት ከራስህ ከቤትህም ይጀምራል። ይህ ደግሞ አባትህ ጽድቅ ትሠራበት ፍትሕ ትፈጽምበት ከሰጠህ ጸጋ ጋር የሚገናዘብ፣ ባስቀመጠልህ መክሊትም የምትጠየቅበት ኃላፊነት ነው።

የምታገባት ሴትም ይህንኑ አውቃ የምምሰማህ፣ የምትከተልህ፣ ፈቃድህንም የምትፈጽም መኾኗን ከአስተዳደጓ ጀምረህ አጥና።

የእንቶኔ ማኅበር አባል ነች፣ ሰንበት ተማሪ ነች፣ ቆራቢ አስቆራቢ ነች አይደለም እዚያ አመጸኛ አድርገው በተለይም ለወንድ ልጅ መገዛት እንደሌለባት ግተው ያሳድጓታል።

ይህ ከኾነ እንደቀደመው አልጫ መካሪ ትኖራለህ፤ በዚያም ይኸው መካሪ ሆዳደር ሆኖ ባፍጢሙ ተደፍቶ እንደሚኖርበት ቤቱ በአደባባይም ሆዳደር ኾነህ መቀጠልህ እርግጥ ነው።

እኔን በዚህ ዙሪያ ሥልጠና ስሰጥ እንዲህ ብሎ የመከረኝ አልነበረምና ጉዳቱን በአንደኛ ተጠቂነት ስለማውቀው እነግርካለሁ። ወይንም የተመከርነው "ተጋገዙ" ከሚል ያለፈ አልነበረም።

አሁን ግን ከዚህ በባሰው ሚናችሁ አባታዊው ማኅበረሰብ የጫነባችሁ እንጂ ይህንና ያንን በልዩነት ሥሩ የሚል ተፈጥሮኣዊ ሥርዓት የለም ይሉናል።

ቆየኝ እጨምርልሃለሁ!

አባወራ

28 Dec, 06:59


ምስኪን ቢልከሰክስ ከስሜት እስኪያደርሰው ከሴት
=====================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ይህ ብዙም ጠልቀን የማንሄድበት የፍኖተ-አባወራ ሥልጠናን ግማሽ የሚወስደው የምስኪን ጠባዕያት ትንታኔና ማብራሪያ ላይ የሚገኝ ነው።

ምስኪን እውነትን ይዞ፣ በስልትና በአመክንዮ ሞግቶ፣ ልምዱንም ተንተርሶ፦ ራሱን ችሎ ከመቆም ይልቅ የሰው ስሜት አድማጭ፣ ጠባቂ፣ ጠንቃቂ ነው።

ይህንንም ደግሞ "ጥሩ ሰው ኹን፣ መልካም ሰው ኹን፣ መንፈሳዊ ሰው ኹን..." በሚባሉ የምክርና አንዳንዴም የሽንገላ ቃላት ከቤት እስከ ሰንበት ትምህርት ቤት(ቤተክርስትያን) ድረስ በማኅበረሰቡም እየተመከረ በተለይ በቤተሰቡ ይበልጡንም በእናቱ ማስጠንቀቂያ ያደገበት ነው።

ስለኾነም እርሱ የእኔ የሚለው፣ ደረቱን ነፍቶ የሚያውጀው፣ በቃላት ገልጦ የሚናገረው፣ በምክንያትና ስልት ሞግቶ፦ የሚቆምለት፣ የሚኖርለትና የሚሞትለት የራሱ የስሜትም ኾነ የፍላጎት እንዲሁም የአቋም ብያኔ የለውም።

ይልቁንስ እንዳደገበት "ጥሩ ሰው፣ መልካም ሰው፣ መንፈሳዊም..." ለመባል የሌሎችን ስሜት ሲያዳምጥ፣ ሲከተል፣ ሲያነሳና ሲጥል ይኖራል።

ለዚህም ነው "ምስኪን የስሜት ልክስክስ ነው" የምለው! እኔ ልጆቼ እንኳን ወንዶቹ ሴቶቹም የስሜት ልክስክስ እንዲኾኑ አላበረታታም! እንደውም እንዲጥሉት እሞግታቸዋለሁ እንጂ እነርሱም እንደዚሁ!

ወንድምዓለም! ምስኪን "ጥሩ፣ መልካምና መንፈሳዊ ሰው" ኾኖ እንዲታይ እንዲያም ይባል ዘንድ የሰውን ስሜት በተለይም የሴቶችን መስማት፣ መከተልና መጠበቅ ጠባዩ ነው።

ልብ አድርግ! ይህ የወንድ ባሕርይ አይደለም! በጭራሽ! ነገር ግን እርሱ የአስተዳደግ በደል አለበትና እንዳደገበት "የጥሩ ሰው፣ መልካም ሰው ኹን አደራህን እንዳታሰድበኝ እንዳታሳዝነኝ" በሚሉ፤ በተለይ የእናት ማስጠንቀቂያ የተነሳ ሰውን ላለማሳዘን ራሱን ረስቶ፣ አቅሉን አጥቶ፣ ሕሊናውን ክዶ እንዲህ ይኾናል።

ስለኾነም በሰዎች ዘንድ ለመወደድ በተይም በሴቶች ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት ወደ እነርሱ የስሜት ሞገድ ቀርቦ፣ ስሜት ለስሜት ተናቦ፣ ይገናዘባል።

በአጭሩ ምስኪን ሴቶችን በጠባይ፣ በመናበብና በመገናዘብ ይመስላቸዋል። ይህ ጠባዩ በሴቶች ዘንድ ቢያስወድደውም ቅሉ እንደ ታናሽ ወንድም ቢያስቆጥረው ቢያስመርጠው እንጂ እንደ ባል በተለይም እንደ አባወራ አያስከጅለውም አያስከብረውምም!

ይኹን እንጂ ከአባወራው ወንድ ይልቅ ምስኪኑ ቁጭ ብሎ ውሎ አድሮም ቢኾን የሴቶችን ሮሮ፣ ወሬ፣ ብሶት፣ ለቅሶ፣ ክስ፣ ጨዋታ፣ ፌዝ ለመስማት ፈቃደኛ ነው።

እነርሱም እንዲህ ያለው ጉዳይ ሲገጥማቸው ከአባወራው ወንድ ወይንም ባላቸው ይልቅ ምስኪኑን ይመርጣሉ፤ የቀደመው ለዚህ ጊዜና ቦታ እንደሌለው ያውቃሉና።

ታዲያ የምስኪን ልክስክስነት በዚህን ጊዜ ይመጣል! ሴቷ ከአባወራው ባሏ ያጣችውን፣ የተከለከለችውን፣ የነፈጋትንም እርሱ ምስኪኑ ሊሰጥ በዚያም ውዳሴና ይኹንታ ቀለቡን ሊሸምት ይቀርባል።

ከሰው ሚስት እየደረሰ "እሺ...፣ እና....፣ ኧረ ባክሽ...፣ አትዪኝም...፣ አያደርገውም...፣ ሂጅ.. ሂጅ...፣ ጉድ እኮ ነው...፣ ሄኖክን ሳውቀው እኮ እንዲህ አልነበረም፣ ይገርማል፣ እንግዲህ ውጊያ ነው፣ መስቀል ነው ተዋጊ፣ አይዞሽ፣ አንቺ ጥሩ ሴት ነሽ፣ በዚያ ላይ የተማርሽ ኮሌጅ የበጠስሽ፣ በእርሱ ላይ መንፈሳዊነት የደረብሽ....." ይላል።

ሊረዳት ቢፈልግ እንኳ አንድ ቀን ጨክኖ ባሏን "ለምን እንዲህና እንዲያ ኾነ?" ብሎ መጠየቅ አይችልም። ያውቀዋላ የራሱን ስሜታዊነት፤ እርሱና እርሷ "ግትር" የሚሉትን የባሏን ስልታዊና ምክንያታዊነት።

እርሷም "እንቶኔ አንተ ባትኖር ለማን እተነፍሳለሁ፣ የውስጤን ስለምትረዳኝም አመሰግናለሁ፣ አንተን የሰጠኝም......." ስትለው የተራበውን ምግብና፣ የፈለገውን ቀለቡን፣ የናፈቀውን ማዕዱን ያገኛል፤ በዚህም ደስስስስ ይለዋል! ምስኪን ነዋ!።

ለምን መሰላችሁ እርሱ እንደ አባወራው ወንድ ወደ ተፈጠረለት ልዕልና፣ ወደ ወንድነቱ ቁና ይወጣ ዘንድ ራሱ ላይ መጨከን አይችልም፤ አይፈልግምና!

ይህንን እኔ የምስኪን ልክስክስነት እለዋለሁ! እንደ ሴሰኛው ሴቷን እስኪተኛት፣ አንድቀንም እስኪማግጥ ያውም፣ እረፍት ለማታገኝበት፣ ትርፉም ጸጸት ብቻ ለኾነበት .....

ስንት ሴቶች በእንዲህ ያለው ምስኪን ልክስስነት ትዳራቸው ፈረሰ፣ ቤተሰባቸው ተበተነ፣ ልጆቻቸውም.... አይ! ምስኪን ልክስክሱ!

"እኔ እኮ ከባሌ ይልቅ እንቶኔ የምለው ሳልናገር ይገባዋል፣ ብነግረው ይረዳኛል፣ እንዳው ሚስቱ ታድላ..." የሚሉ ሴቶች፣ የሚባልላቸው ወንዶችስ አልገጠሟችሁም።

አዎን! እንግዲህ እነ "እንቶኔ" የስሜት ልክስክስ መኾናቸው ነዋ! አንተም ብትኾን ያው ነህ! ይኹንታና ውዳሴ ቀለቡ ምስኪን ከሰው በተለይም ከአባወራው ሚስት ደርሶ አድማጭ ኾኖ በስሜት የሚልከሰከስ እንዲህ ነው!

ሴሰኛ ከስሜት ቀጥሎ፣ ስሜትን ጨምሮ አንድም በስሜት መልከስከስ ላይ የወሲብ ልክስክስነትን የደረበ ወራዳ፣ ውርደቱንም ከከብር የቆጠረ ነው!

ጉዳዩ ሰፊና ጥልቅ ነው! በተለይ በነገው የፍኖተ-አባወራ ሥልጠናችን ላይ ፦ የምስኪን ሐተታና የጠባያቱ ትንታኔን በጥልቀት እናየዋለን!

ዛሬ በማኅበረሰባችን በተለይም በቤተክርስትያን የምናየው የምስኪን ብዛት፣ የትዳራችን ፈተና፣ የማኅበረሰባችን ውድቀት የእነዚህና ሌሎችም ድምር ውጤት ነውና!

አባወራ

27 Dec, 06:49


ልክስክስ መኝታ አርክስ ትዳር አፍርስ
=======================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

በዚህ ዐውድ ልክስክስ የምለው ሴሰኛውን ወንድ ነው። እርሱም የራሱ የኾነች ሴት(ሚስት) ብትኖረውም ባትኖረውም የሌላ ከኾነችው ጋር የሚዳራ አልያም ከአንዷ ጸንቶ የማይኖረው፣ ከትዳሩ ሌላም የሚማግጠውን የሚልከሰከሰውን ይኸውም "ጀብድ ወንድነት" የሚመስለው ነው።

ወንድነት መክሊቱን፣ የወንድነት ጨውነቱን፣ የወንድነት ጸጋነቱን፦ያላወቁ፣ ያልተማሩ፣ ያላዩ፤ አንድም የወንድነት መክሊትነቱን፣ የወንድነት አልጫዋን ዐለም ማጣፈጫ ጨውነቱን፣ ግዳጅ መፈጸሚያ ጸጋነቱን የሚያሳውቃቸው ያጡ፣ የሚያስተምራቸው ያላገኙ፣ የሚከተሉትን ፈለግ የጣለላቸው አርአያ የሌላቸው እነርሱ በተሰጣቸው ጸጋ የመበደላቸው ዕድል ሰፊ ነው።

ከእነዚህም መካከል በተለይ አሁን ባለንበት ጊዜና ዘመን ላይ ከሚታዩት ጠባያት (ልብ አድርጉ የወንድ ልጅ ባሕርይ ነው አላልኩም ጠባይ እንጂ) መካከል ልክስክክነት ወይንም ሴሰኝነት ከቀዳሚዎቹ አንዱ ነው።

ጽድቅ ይሠራበት ዘንድ የተሰጠውን ወንድነት እንዴት ሊሠለጥንብ፣ ሊበለጽግበትና መርቶም በጎውን ሊፈጽምበት እንዳለው የሚያሳየውን አባት በተለይም በእኛ ዐውድ አባወራ ያላገኘ ትውልድ ለስሜቱ በባርነት ለማደር ይገደዳል።

በዚህ ላይ ደግሞ መዳራትን በሚያስተምሩን ዘፈኖች ታጅበን፣ ሽርሙጥናን እንደ ጽድቅ፣ ፈትነትን እንደ ጀብድ፣ ዲቃላ መጎተትንም ዘመናዊነት አድርገው ከሚያሳዩን ፊልሞችና ማስታወቂያዎች ጋር ስንደመር ልክስክስነት(ሴሰኝነት) ወግ ይኾንብናል።

ወንድምዓለም! ዛሬ በስሜቱ ላይ መሠልጠን የተሳነው ወንድ ማግኘት እጅግ እየከበደ ነው። ተፈጥሮአችን ከፈጣሪያችን አንጻር የምንረዳበት መንፈሳዊውን እውቀት ከሚግቱን ዘንድ እንኳ ይህ ታላቅ ፈተና እየኾነ ነው።

ስለኾነም ሰውን ስትቀርብ በወዳጅነትም ስትዘልቅ ከሚነግርህ "ጣፋጭ" ወሬ፣ ከሚተረተር አንደበቱም ይልቅ ተግባሩን፣ ምግባሩን፣ ውሎውንም መርምር።

በጭራሽ "መንፈሳዊ ነው፣ ቆራቢ አስቆራቢ ነው፣ ሰባኬ ወንጌል ነው" በሚል እንዳትሸወድ። ሲልከሰከስ ካየኸው እርሱ ማንም ይኹን ማን ለምን የእናትህ ልጅ አይኾንም ተለይ!

ጥቂት የማይባሉ ወንዶች መንፈሳዊነትን ተገን አድርገው ከክብር ያወረዷቸው፣ ወንድ ጠል እንዲኾኑ ያደረጓቸው፣ ላያገቧቸው ነካክተው የተውአቸው፣ ለሴታቆርቋዡ ርዕዮት-ዐለም(Feminism) አሳልፈው የሰጧቸው፣ አሁንም በቤተክርስትያን ውስጥ ሴታቆርቋዥ (Feminist) እንዲኾኑ ያበረታቷቸው፦ እነዚሁ "መንፈሳዊ ነን" ባይ፦ ሴታውል፣ ልክስክስ፣ ሴሰኛ ወንዶች ናቸው!

ከሰው ይልቅ ለእንሰሳ በተለይም የሰው የቅርብ ወዳጅ ለሚባለው ውሻ የመልከስከስ ጠባይ ባሕርያዊ ነው። ለምን መሰላችሁ በእጁ፣ በእግሩ ዳሶ ይበልጥም ደግሞ በአንደበቱ ተናግሮ በጆሮው ሰምቶ የከባቢውን ነገር መረዳት አይችልምና ያገኘውን ሁሉ ወደ አፉ ወይንም በምላሱ ይለክፋል።

ይህንንም የውሻ ባሕርይ በሰው ጠባይ ሚዛን ሰፍረነው "ልክስክስ" አልነው እንጂ፤ በውሾች ዐለም የውሻ ልክስክስ የለውም፤ መገናኛ፣ መግባቢያ፣ መለያ ጠባያቸው እንጂ ነውና!

እኛ ግን "በልቶ ላይበላው፣ ጠጥቶ ላይጨርሰው ይህንና ያንን ለከፈበኝ፣ ይሄ ልክስክስ ውሻ እንላለን" ንግግሩ ከብስጭት የመጣ ስሜታዊ ነው። ድሮም እርሱ የለካከፈው ሁሉ ተፈጥሮአዊ ጠባዕይ ኾኖበት እንጂ ሊበላው ወይንም ሊጠጣው ሽቶ አይደለም።

ኾኖም ግን የዚህ የውሻውን ተፈጥሮአዊ ባሕርይ ጠባያቸው ያደረጉ ከዚህም ጠባይ የተነሳ እንደ ውሻ የሚልከሰከሱ በርካታ ልክስክስ ወንዶች አሉ።

ሳተናው!
ልክስክስ ወንድ፣ ከሴት ጭን መሐል መዋል ሱስ የኾነበት ሴሰኛ ወንድ፣ ሴት የተባለችውን ሁሉ መለካከፍ (ልክ እንደ ውሻ ምሳሌያችን)፣ እስኪለካክፋትም እርሷን ማወደስና ማቆለጳጰስ ጠባዩ ነው!

እርሱ ግን ማንም ይኹን ማን በቅርብህ እንዲኾን አትፍቀድ! ከእርሱ ለመለየትም ምንም ዓይነት ማስጠንቀቂያም ኾነ ማሳሰቢያ አያስፈልግህም! "ንስሃ ገባሁ ቆረብኩ" ቢልህም እርሱን በሰማይቤት ከሚመለከተው አካል ጋር ይነጋገርበት እንጂ በዚህ ሳለ ግን አሁንም ምግባሩን ዓይተህ ተጠንቀቅ!

ድመት መንኩሳ ዐመሏን አትረሳ! እንዲሉ "አሁንማ አግብተን ወልደን፣ ቆርበን አስቆርበን" እያሉ የሰው መኝታ የሚያረክሱ፣ ትዳር የሚያፈርሱ ልክስክሶችን በወሬ ሳይኾን በተጨባጭ አውቃለሁና እንዲህ አልኩህ!

ዐመል ክፉ ነው! መንፈሳዊ ትምህርታችን ትልቁ ጥቅሙ አባታችንን ማየት፣ ከእርሱም ጋር መኖር የሚያስችለንን ስብዕና(character) ለመገንባት፣ በተለይም ጽድቅ ልንሠራበት የተሰጠንን መክሊት(ወሲቡንም ጭምር) ልንሠለጥንበት ነበር። አብዛኞቻችን ግን ልማዳዊ ነንና ከነ መጥፎ ዐመላችን እንግበሰበሳለን።

ከምስኪንነት ወደ አባወራነት የሚወስደውን መንገድ በተፈጥሮኣዊ እውቀት ለማይሄድበት፣ መሄድ የተሳነውም አላዋቂ ወንድ ከሴሰኞች አዘቅት ሊወድቅ ይችላል።

ሳተናው!
በአባወራነት እየሠለጠንክ በወንድነት ልዕልና ላይ ስትሰፍ ሴሰኞች ሊቀርቡህ አይችሉም፣ አይፈልጉም፣ አይገባቸውም! እነርሱ ወዳጆችህ አይኾኑምም!

መሠረታዊው የአባወራ ብያኔ እርሱም በራስ ላይ መሠልጠኑ ከእነርሱ ዋነኛ መለያ ጠባይ ጋር ይጋጫልና። ኾኖም ግን "እኔ አባወራ ነኝ የሀያ ዐመት ወዳጄ ግን ሴሰኛ ነው ምን ባደርግ ይሻለኛል?" ብትለኝ፦ አንተ መጀመሪያውኑ አባወራ አልኾንክም እልሃለሁ።

አባወራ ባለበት ሴሰኛ ቦታ የለውም! አንድም አባወራ በኾንክበት ጠባዕይ ሴሰኛ አይወዳጅህም! አንድም አባወራነት ሴሰኝነትን ማርከሻ፣ መደምሰሻ፣ መፈወሺያ፣ ማሸሺያ እንጂ መታገሺያ አይደለምና!

ወንድምዓለም! ልክስክስ ወንዶችን አውቃለሁ! ሴሰኛ ወንዶችን በተለይም ለረጅም ዓመታት በሠራሁበት የባንኪንግ ኢንደስትሪ አስተውያለሁ!

እነርሱ በጋብቻ የተቀደሰውን መኝታ የሚያረክሱ፣ የብዙዎችን ትዳር ያፈረሱ፣ ጭቃ-ዐመላቸውን ታጥበው እንኳ የማይረሱ ኾነው አግኝቻቸዋለሁና ተለያቸው!

ትዳር መሥርተህ፣ ልጆችን ወልደህ፣ የራስክን ልጆች(ልክስክስ ባለበት ልጆችህ ያንተ ያለመኾን ዕድል አላቸውና) መክረህ፣ ገስጸህና ቀጥተህ ማሳደግ፣ ትውልድን ማነጽና ሀገርን መገንባት ከፈለግክ፦ ልክስክስን ከቤትህ፣ ሴሰኛን ከትዳርህና ከወዳጅነትም ለየው!

ታናሼ! እርሱ ማንም ይኹን ማን፣ ለምን የእናትህ ልጅ አይኾንም ልክስክስ ጠባዩን ያወቅክበትን፣ ሴሰኛ ዐመሉን የተረዳህበትን ሰው፦ ዛሬ አሁን ተለይ!

ድመት ምን ብትመነኩስ እርሷ ፊት ወተት አስቀምጠው እንደማይነሱ፤ በመኝታ አርክሱ፣ ትዳር አፍርሱ ልክስክስ ፊትም እንዲሁ ነው!

መቼም የአባወራ ገጽን የሚያነብ ሴሰኛ፣ የሚከተለኝም ልክስክስ የለም! እኔ ሴሰኛ ልክስክስ ወዳጅም የለኝም! ሴሰኛ ተኝቶ መጫወት እንጂ ለቁምነገር ስልቹ ነውና!

ድመት ስግግ ብላ እየታከከችህም ስትመጣ ዐመሏን የተወች፣ አሁንማ የመነኮሰች፣ ስጋም ኾነ ወተት የተጠየፈች ትመስላለች።

ነገር ግን የተዘናጋህበት አንድ ብዙ አይደለም አንድ አጋጣሚ ስታገኝ ግን፤ ላንተ ረፍዷል፣ ወተቱ ተደፍቷል፣ ስጋው ተጠልፏል፣ ዕቃው ተለክፏል።

ሴሰኛና ልክስክስ ወንዶችንም ስታቀርብ እንዲሁ ይኾናል! በምን እንለያቸው (እንወቃቸው) በሥልጠናችን በዝርዝር የምናየው ይኾናል!

አባወራ

27 Dec, 03:54


https://youtu.be/AGE4UUDqvhY?si=zBWBTHp_f2LP0UNW

አባወራ

26 Dec, 09:16


ጎበዛዝቱን መክሊት ቅበሩ ትውልዱን በባርነት እደሩ
==================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

አሁን ያለንበት ጊዜና ዘመን ላይ ያለው ትውልድ ነቀርሳ ኾኖ የሰውን ልጅ፣ ተቋማቱንና የተጋመዱበትን የፍቅር ሠንሰለት እየበከለ ስላለው ማርክሳዊ እሳቤ ሊያውቅ ይገባል።

ምክንያቱም ብዙኃኑ ካለማወቅ የዚህ በሽታ ተሸካሚ(vector) ኾነው ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንና የገቡባቸውን ማኅበራዊ ተቋማት እየበከሉ ነውና።

ከመሠረታዊው፣ ከቀዳሚው፣ ከጥንታዊውና በአባታችን ፈቃድ ከተወጠነው፣ ሌሎች ልንገነባቸው ላለነው ተቋማት መነሻ መሠረት፣ መደርደሪያ ጡብ ኾኖ ከሚያገለግለው፦ ትዳር፤ ጀምሮ ሁሉንም መስተጋብር በጨቋኝና ተጨቋኝ፣ በከበርቴና ጭሰኛ መነጽር እንድናይ የሚያደርገን ይኸው ማርክሳዊ ልክፍት፣ ነቀርሳ የሚኾንም በሽታ ነው!

ይህንን "የመደብ ልዩነት ሊያስተካክል" ከሰይጣን የተሻረከው ማርክስ የጠነሰሰው የርዕዮት-ነቀርሳ እነኾ ተባዝቶና ተሰራጭቶ ባሕላዊ እሴቶቻችንን፣ ማኅበራዊ ተቋማቶቻችንን፣ መንፈሳዊ ሚዛናችንን፣ እውነትን የምንዳኝበት ሕሊናችንን፣ አስተዳደራዊ (ፖለቲካዊ) ትንታኔዎቻችንን፣ ሳይቀር በርዞታል!

ማርክስ ያ እርሱ የጠላውን "የመደብ ልዩነት" ለማጥፋት "'ከበርቴውን' ሀብቱን መዝረፍ፣ 'ጨቋኙን' ሥልጣኑን መግፈፍ ነው" ብሎ አምኗል። ይህንንም የርዕዮተ-ዐለሙ ደጋፊና ተከታዮች ከየቀድሞዋ ሶቪየት ሕብረት ጀምሮ፣ ቻይና፣ ኢትዮጵያንም ጨምሮ ሌሎች ሀገራት ከአንድ መቶ ሚሊዮን በላይ የሰው ነፍስ ሲያስጠፋ እንደ ኢትዮጵያ ባሉት ሀገራት ደግሞ እንደገና እያገረሸ ይገኛል።

የዚህ ነቀርሳ እጅግ አስከፊው ጥቃት ግን መድኃኒቱ ከኾነች ቤተክርስትያን ገብቶ፣ ባፍጢማቸው የተደፉ ታማኝ ሆዳደር ምንደኞችን ተፈናጦ፣ ትውልዱን፦ ለዘር ማንዘሩ ለሚተርፍ ጥላቻ፣ እርስ በእርሱ እንዳይተማመን ለሚያደርገው ፍራቻ፣ ዘር እንኳ መቀጠልና ትውልን መገንባት ከማያስችለው ዳርቻ ገፍቶ ማድረሱ ነው።

ይህንኑ ሸፍጥ የሚሰውሩበት አስመሳይ መፈክራቸው፣ አጣፍጠው የሚናገሩበት ከንፈራቸው፣ ትውልዱን የሚደልሉበት ምላሳቸው፦ ለተጨቆኑት፣ ለተገፉት፣ ለአቅመደካሞቹ ሲሉ በተለይም በሴቶችና ሕጻናት ይበልጡን ደግሞ በሴቶች ላይ የሚደርስ ጾታዊ ጥቃት ስም መሰወራቸው ነው።

ልብ አድርጉ! ደግሜ ደጋግሜ እነግራችኋለሁ ገና በወጣትነቱ ከሰይጣን የተሻረው ካርል ማርክስ፦

🌟 ካፒታል ሲል የገለጠውን ሀብትን ሀብታሙንም ለማጥፋት፦ በስሙ ሀብት የሚሰበሰብለትን ቤተሰብን፣

🌟 ቤተሰብንና የቤተሰብን መዋቅር እነርሱንም የበየናቸውን ተቋም ለማጥፋት፦ ኃይማኖትን(ቤተክርስትያንን)፣

🌟 ቤተሰቡን፣ ማኅበረሰቡን፣ ቤተክርስትያኑንና ሀገሩን ለማጥፋት፦ ስለ እነርሱ ሲል የሚኖር የሚሞትላቸውን ቤተሰብ መሥራቹን ወንዱን ጎበዛዝቱን መጎሳቆል፣ መስለብ፣ ማለጭ እንደኾነ ሲያውቅ፤

🌟 ወንዱን ከወንዱም የወንድ ቁና ጎበዛዝቱን(አባወራውን) ለማጥፋት ደግሞ በእርሱ ላይ ወይዛዝርቱን ማሳመጽ ውጤታማ እንደሚኾን አውቆ እንክርዳድ ዘሩን በወቅቱ ቢዘራ፤ ዛሬ በእኛ ጊዜና ዘመን ላይ ምናልባትም ካሰበወና ካቀደው በላይ መልካሙን የስንዴ ማሳ ውጦለታል።

ወንድምዓለም! ትውልዱ ከትውልዱም ወንዱ አባቱ አውቆ፣ ሰፍሮ፣ ቆጥሮ የሰጠውን ጸጋ፦ መክሊት ወንድነቱን እንዲቀብር ከተኩላ ጋር ከተስማሙ ምንደኛ እረኞቻችን ዘንድ በግልጥ መጥቷል!

ድሮም በጥርጣሬ የሚታዩ የቤተክርስትያን ባለድርሻ አካላት ዛሬ በተጨባጭ፣ በግልጥ፣ በአደባባይ ትውልዱን ሊበላ ከቋመጠው ነጣቂ ተኩላ ጋር በጎቻቸውን እንዴት አድርገው ከዋሻው በፈቃዳቸው፣ እያስጨበጨቡና እያስዘመሩ እንደሚያመጡት መክረው፣ ዘክረው፣ አቅደውም ጨርሰዋል!

ጎበዛዝቱ ወንዶቻችን መክሊታቸውን መቅበር እንዳለባቸው፣ አልጫነት መንፈሳዊነት እንደኾነ፣ አሰስነታቸውም ጽድቅ እንደሚሠራ ሊማሩ መርሐግብር ተዘርግቶላቸዋል።

ጎበዛዝቱ በትዳር ውስጥ ያለ ከአባታቸው የተሰጣቸውን ሥልጣን "ማርክሳዊው ነቀርሳ ፍሬ ያፈራ ዘንድ" እንዲጥሉት፣ እዚያ የጣሉትንም ወንድነት መክሊታቸው ማኅበረሰብንም ኾነ ቤተክርስትያንን መታደግ እስካይችሉ ድረስ እንዲጠየፉት ይደረጋሉ!

በዚያም ያለጨ፣ ወኔ ያጣ፣ ሐሞቱ የፈሰሰ፣ ታይታና ጭብጨባ የሚወድ ትውልድ በቅሎ፦ በእናትና ሚስቱ ሞት፣ በእቶቹና ልጆቹ መከራና ዋይታ ላይ ነጭ ለብሶ እየተረማመደ፣ በዝማሬም ምድሪቷን እያንቀጠቀጠ ወዶና ፈቅዶ ወደ ባርነቱ ሊገባ ይቸኩላል!

ከትውልዱ ግን ይህን ማን አስተዋለ!

እኛ ግን በፍኖተ-አባወራ ትውልዳችንን ከእርሱም ወንዶቻችንን አባታቸው የሰጣቸውን ጸጋ አውቀው፣ ወንድነት መክሊታቸውን ጠብቀው ሠልጥነውበትና በልጽገውበት ጽድቅ እንዲሠሩበት ፍትሕ እንዲያሰፍኑበት የምናሳያቸው አባወራዎች ነን!💪

አባወራ

26 Dec, 04:13


ወንዶቹን የሚሰልብ ማኅበረሰብ ባርነቱን መርጧል
===============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

የሶሻሊዝም በሽታ የማርክሳዊው ነቀርሳ ከትውልዱ ወንዱን መስለብ በዘላቂነት የእድገትና የብልጽግና ጉዞውን ማጨናገፍ ብቻ ሳይኾን ባርነቱንና ሞቱንም አሳምኖ የሚሰጥ ነው።

ማርክሳዊው ሶሻሊዝም እግዚአብሄር በአምሳሉና በአርአያው የፈጠረውን ሰው፣ ማኅበረሰቡንም ምንጊዜም ከሁለት እነርሱም ጨቋኝና ተጨቋኝ እያለ የሚቦድን ከፋፋይ ርዕዮተ-ዐለም ነው።

በዚህ መርዘኛ እንደነቀርሳም የሚበዛ፣ የሚባዛ፣ ተስፋፍቶም ተሸካሚውን በቁም ከሰውነት ወደ እንሰሳነት አጎሳቁሎ የሚጥል ልክፍት ትዳርን ቤተሰብን እንደሚያፈርስበት ካርል ማርክስ እርግጠኛ ነበር።

ይኸው ዛሬ የዘራው በቅሎ፣ አቆጥቁጦና አሽቶ ፍሬም አፍርቶ አጭደንና ወቅተን ከእያንዳንዳችን ቤት እያስገባነው ቤታችንንም እያፈረስንበት ይገኛል።

ወንዱ ጨቋኝ ሴቷ ተጨቋኝ ተደርጎ በተጋትነው ትርክት! በዚህ ትርክት ወንዱ ከእናትና ከአባቱ ቤት ጀምሮ ራሱ እስከመሠረተው ትዳሩ ድረስ ወኔ-ቢስ፣ ሐሞት የለሽ አልጫ እንዲኾን ራሱ ማኅበረሰቡ ይሠራል።

እጅግ የሚያሳዝነው ይህንኑ ማርክስ ከሰይጣን ጋር ተሻርኮ የጻፋቸውን ትርክቶች ተንተርሰው የበዙና የተባዘቱ ተረፈ ማርክሳዊ ትዳር አፍራሽ፣ ቤተሰብ በታኝ፣ ወንዱን አምካኝ በተለያዩ ጊዜያት የሚነሱ መመሪያዎችን፤ ለሆዳቸው ባደሩ፣ ጥቅማቸው እንጂ የትውልዱ ድኅነት በማይገዳቸው ምንደኛ እረኞች አማካኝነት ወደ ቤተክርስትያን መምጣቱ ነው።

ወንድምዓለም! ብዙዎች ገፍቶ፣ ጎትቶ ባፍጢም ለደፋቸው ለሆዳቸው፤ በካባና ላንቃ በማዕረግም ብዛት ለተንዠረገገ ስማቸው የሚጨነቁ እንጂ አሁንም ስለ ትውልዱ የማይገዳቸው ኾነዋል።

ልጆቻችንን በተለይም ራሳቸውን፣ ሚስታቸውን፣ ልጆቻቸውን፣ ቤተሰባቸውን፣ ማኅበረሰባቸውን፣ ቤተክርስትያናቸውን፣ ሀገራቸውን ሊጠብቁ ያላቸው፤ አባታቸውም ይህንኑ እንዲፈጽሙ ጸጋውን የሰጣቸውን፣ መክሊቱንም ያበዛላቸውን ወንዶቻችንን የሚሰልቡ በጠላት የተዘሩ ትምህርቶችን መርምረን ልናስወግዳቸው ይገባል።

ሳተናው!
ወንዶቹን የሚሰልብ ማኅበረሰብ፣ ወንዶቹን አሰስነታቸውን አጽድቆ ከጸጋቸው የሚለያቸው ማኅበረሰብ፣ ወንዶቹን አልጫነታቸውን "መንፈሳዊነት ነው" እያለ መክሊታቸውን የሚያስቀብራቸው ማኅበረሰብ ዘሩን መተካት የማይችል ዘረ-ቢስ ኾኖ ይጠፋል!

አንድም ወንዶቹን የሚሰልብ ማኅበረሰብ፣ ወንዶቹን አሰስነታቸውን አጽድቆ ከጸጋቸው የሚለያቸው ማኅበረሰብ፣ ወንዶቹን አልጫነታቸውን "መንፈሳዊነት ነው" እያለ መክሊታቸውን የሚያስቀብራቸው ማኅበረሰብ ባርነትን ወዶና ፈቅዶ መርጧል!

አንድም ወንዶቹን የሚሰልብ ማኅበረሰብ፣ ወንዶቹን አሰስነታቸውን አጽድቆ ከጸጋቸው የሚለያቸው ማኅበረሰብ፣ ወንዶቹን አልጫነታቸውን "መንፈሳዊነት ነው" እያለ መክሊታቸውን የሚያስቀብራቸው ማኅበረሰብ ሞቱን ሽቶ ገዳዮቹን ይቀልባል!

ወንዶቻችንን የመስለብ ሥራ በሰፊው እየተሠራ ነው! ይታያችኋል ግን? እየበዛ የመጣው የወንዶች መሐንነት መንስዔው ይታወቃችኋልን?

ከታያችሁ በኋላስ? ከዚያስ? ቁጭ ብሎ ማዘን ማላዘን፣ መነፋረቅ?

ወይንስ "ድሮም ብዬ ነበር?" ለማለት አፍን አሹሎ፣ ከንፈርን አሞጥሙጦ መቀመጥ!

እኛ ግን በፍኖተ-አባወራ ለትውልዳቸው የማይራሩ፣ ለልጆቻቸው የማያዝኑ፣ ለመንጎቻቸው የማይጨነቁ ይልቁንስ ገንዘብና ዝና አሳደው ወንዶቻችንን የሚያኮላሹ፣ የሚሰልቡ ፍዝ፣ ድንዝዝና በድን እንዲኾን ከጠላት ጋር የተሻረኩትን ሴራ እየገለጥን ልጆቻችንን እናጎብዛቸዋለን!
💪💪💪

አባወራ

24 Dec, 03:35


https://youtu.be/szw0BalX3bY?si=00YIwRqdwzxR4vkh

አባወራ

23 Dec, 09:09


ትውልድን ከታቀደለት ባርነት ወንዱንም ከተጠመደለት አልጫነት መታደግ በተግባር

አባወራ

21 Dec, 09:02


ወንዶቻችንን ሴታሴት ማድረጉ ጥፋትን ያባብሳል
============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ወንዶችን ሴት ማድረግ ስል ጠባያዊ መገለጫቸውን ሴታሴት ማድረጉን፣ እንደ ሴት እንዲያስቡና እንደ ሴት እንዲኖሩ ማስተማርና ማበረታታቱን ነው።

በእርግጥ ሴት መኾን (ሴታሴትነት) ምንም ተፈጥሮአዊ እንከን የሌለበት፣ ስለመልካምነቱም ሰጪው አባታችን የመሰከረለት፣ እኛ ወንዶቹም እናቶቻችን፣ እህቶቻችን፣ ሚሰቶቻችንና ልጆቻችን ላይ ስናየው የምንወደው ተፈጥሮ ነው።

ነገር ግን ሴታሴት ጠባይ በሴት ላይ እንጂ በወንድ ላይ አያምርም፣ አይኾንም፣ ጽድቅን አይፈጽምም፣ ግዳጅ አይወጣም፣ ሴቷን አይማርክም፣ አልፎ ተርፎም አጥፊ በዳይም ይኾናል።

ምክንያቱም መጥፎ ጠባያትን የሚያሳዩ ወንዶች መልካምና ጠንካራ ወንዶች የሚኾኑት በመጥፎ የተገለጡበት ወንድነትን ጠባያቸውን አስወግደው ሲጥሉ ሳይኾን እርሱ ላይ ሠልጥነው ጽድቅ እና ፍትሕ ሲፈጽሙበት እንጂ ነው።

አንድ ወንድ ልጅ ተፈጥሮአዊ ሰውነቱ(አእምሮውም ኾነ ሌላ የሠራ አካላቱ) የወንድ፣ እድገ-ንጥሩም እንዲሁ ወንድ እንዲኾን፣ ወንዳወንድም ኾኖ እንዲገለጥበትና የተፈጠረለትን ዓላማ እንዲፈጽምበት የተሰፈረ ነው።

በእርሱ ላይ መሠልጠን ሲገባው፤ አንድም በእርሱ ላይ ይሠለጥን ዘንድ ወላጅ አባቱ ሊያሳየው ሲገባው፣ አንድም ሳይጠይቅና ሳይለምን አባቱና አምላኩ ጽድቅ እንዲሠራበት በሰጠው ጸጋ ላይ ማኅበረሰቡ ሊያሠለጥነው ሲገባው መኮነኑ ራሱ ኩነኔ ነው።

ከዚህ የሚከፋው ደግሞ መኮነኑ ሳያንስ ሽልጥልጥነትን ከምታበረታታው ዐለም ጋር ተባብረው የሴት ጠባይን በጽድቅና በዘመናዊነት ስም እንዲለብስና እንዲላበስ ማድረግ ተፈጥሮውን ይበልጡንም ፈጣሪ አባቱን መናቅ ነው!

ሰምታችኋል!

ዛሬ ልጆቻችን የሚማሩበት ትምህርት ቤት፣ መጫወቻዎቻቸው፣ ፊልሙ፣ ድራማው፣ ማስታወቂያው፣ መዝሙሩ፣ ስብከቱ፣ የዐውደ ምሕረት መድረኩ፣ መርሐግብሩ እናሌሎች ኁልቁ መሳፍርት የሌላቸው ክንውኖች ወንዶቻችንን ሴታሴት እያደረጓቸው ነው።

ጭራሽ አሁንማ! የትዳርና የጾታዊ ጥቃትን ሊያስተምሩ በቤተክርስትያን የሚዘረጉ መርሐግብሮች ዐይን አውጥተው የወንዱን ተፈጥሮ ኮንነው፣ የሴቷን ባሕርይ አጽድቀ፣ እርሷን እንዲመስል ያስተምሩታል።

ወንዱ ወንድነቱን ጠልቶ መኾን የማይችለውን ሴታሴትነት፤ ሴቷን ዐይቶ እንዲኖር መመሪያ አዘጋጅተው ስምምነት ተፈራርመው አምጥተዋል!

ይህ በጭራሽ እንዲኾን አትፍቀዱ!

የትውልድ መረንነት፣ የመሪዎች አንባገነንነት፣ የእረኞች ምንደኝነት፣ የመምህራን ሆዳደርነት፣ የጎበዛዝቱ ሥርዓት አልበኝነት፣ የጎረምሶቹ ሴት ደፋሪነት፦ እየበዛ የሚመጣው ከወንዶቻችን ዘንድ ወንዳወንድነታቸው አይሎ አይደለም!

ይልቁንስ አባታቸው ጽድቅ ሊሠሩበት በሰጣቸው ወንድነት ላይ አልሠለጥንበት ብለው ከልክና ከአግባቡ አጉድለውት፣ ከኃላፊነቱም ሸሽተው እንጂ!

በተመሳሳይ መልኩም አልጫ፣ ጎስቋላ፣ ሽልጥልጥ፣ እና ምስኪን ወንዶች ክፋትን፣ ጥፋትን፣ ሙስናን፦ ከቤተሰባቸው፣ ከማኅበረሰባቸው፣ ከቤተክርስትያናቸው፣ ከሀገራቸውም ማራቅ አይችሉም።

አንድም ለቤተሰባቸው ማቅረብ፣ ሚስታቸውን ከተፈጥሮኣዊ ፍላጎቷ አሳርፎ ምርጥ-ዘር መስጠት፣ ለልጆቻቸው የጥንካሬ፣ የሥልጣኔና የኃላፊነት አርአያ መኾን፣ ትዳራቸውንም ኾነ ማኅበረሰብን መምራት አይፈልጉም፤ አልሠለጠኑምና አይችሉምም!

አሁን ባለንባት ዐለም አንባገነኖች የሚፈነጩት፣ ማጅራት መቺዎች የተበራከቱት፣ ሴት አስገድዶ ደፋሪዎች የተበራከቱት፣ ሆዳደር እረኞች የፋነኑት በማኅበረሰቡ ውስጥ ያለው ወንዳወንድነት አይሎ አይደለም!

በአልጫ፣ ጎስቋላ፣ ደካማ፣ ምሲንም ወንዶች መበራከት፤ ይኸውም ጎዶሎ ጠባያቸው እንደመንፈሳዊነት፣ ዘመናዊነትና ጽድቅ በየተቋማቱ በተለይም በቤተክርስትያን እየተሰጠ መምጣቱ ነው።

በዚህ ድብልቅልቅ መካከል፣ ከጾታ ግራ መጋባቱ መካከል፣ ትውልድ በአልጫነት ወደ ባርነት በመንጋ ከሚነዳበት መስክ ግን አንድ ለየት ያለ ንቅናቄ ተወለደ!

እርሱም አባወራነት ነው!

በፍኖተ-አባወራ ትውልዱ በተለይም ራሱን፣ ሚስቱን፣ ቤተሰቡን፣ ማኅበረሰቡን፣ ቤተክርስትያኑንና ሀገሩን ሊመራ ያለው ወንድ ወንዳወንድ ኾኖ በድፍረት፣ ጥንካሬና ሥልጣኔው ጽድቅ እንዲሠራበት ፍትሕ እንዲያሰፍንበት ይሠለጥናል!

አባወራ

21 Dec, 06:07


ወንዶቻችንን ወንድነታቸውን መኮነን የምንደኛ እንጂ የእረኛ ጠባይ አይደለም
=========================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ትዳር የሚመሠረትበት፣ ቤተሰብ የሚቆምበት፣ ትውልድ ቅጥ የሚይዝበት፣ ሀገር የምትገነባበት፣ ተቋማት የሚመሩበት፣ ፍትሕ የሚሰፍንበት፣ ጠላት የሚርቅበት፣ ዘር የሚዘራበት ወንድነት ነው።

አሁን እርሱ የሚኮነንበት ጊዜና ዘመን ላይ ነን! ብዙ በጣም ብዙ ያላወቃችኋቸው የአምልኮ መልክ ሸፍጠኞችያላቸው ግን ቃሉን የካዱ ሸፍጠኞች በተለያዩ ጥቅማ ጥቅምና ፍላጎት ተለጉመው በጠላት እየተጋለቡ ነው።

ቀኑ ሲደርስ በመረጃ አጠናክረን የምናወጣቸው እንደ አስፈላጊነቱ ደግሞ በሚያጠፉት ትውልድ ጎን ቆመን ከሕግ ፊት የምንፋረዳቸው ይኾናሉ። ለጊዜው ግን "ቤተሰብ ላይ፣ ትዳር ላይ፣ ልጆች ላይ እንሠራለን" እያሏችሁ ልጆቻችንን በተለይም ወንዶቹን ወንድነታቸውን መኮነን እያስተማሯቸው ነውና ጥንቃቄ ይኑራችሁ።

በዚያም ደግሞ ልጆቻችን ራሳቸውን እስከ መጥላት፣ ተፈጥሮኣቸውን እስከ መጠየፍ ብሎም እንዲያ አድርጎ የፈጠራቸውን የሚወዳቸውንም አባታቸውን እስከ መተው ይደርሳሉ።

እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ እውነተኛውን ተፈጥሮ በመንፈሳዊ ማያችን ሊያሳዩን፣ ሊገልጡልን የሚገባቸው መምህራንም የዚህ እኩይ ዓላማ አስፈጻሚና አሳላጭ መኾናቸው ችግሩን ያከፋዋል።

ትውልዱ ወንድ እንዲወጣው! ከወንዱም የወንድ ቁና አባወራ እንዲሠለጥንበት አይፈለግም! ልብ አድር! ምን ዓይነት አባት፣ ምን ዓይነትስ እረኛ፣ ምን ዓይነትስ እናት? ምን ዓይነትስ ሚስት ናቸው የወንዶቻቸውን፦
☀️ ስልብነት፣
☀️ ዘረ-ቢስነት፣
☀️ ወኔቢስነት፣
☀️ ጎስቋላነት፣
☀️ ስልባቦትነት፣
☀️ ልፍስፍስነት፣
☀️ አሰስነት፣
☀️ አልጫነት፣
☀️ አላዛኝነት፣
☀️ ነፍራቃነት፣
☀️ ሆዳደርነት፣
☀️ ባርነት፣
☀️ ሽልጥልጥነት... የሚፈልግ፣ የሚመኝ እንዲኾንም የሚያስተምር። እርሱ ጠላት አልያም ከጠላት የተዋዋለ ቅጥረኛ ምንደኛ ቢኾን እንጂ!

ትውልዱ ለምንምድን ነው፦ ንክር-ያለ ምስኪን፣ የወጣለትና የተዋጣለት አልጫ፣ ወደ ባርነቱና ሞቱ ወዶና ፈቅዶ ሲኾንም እያጨበጨበ እየዘመረ የሚነዳ እንከፍ እንዲኾን የሚፈለገው?

ወንድምዓለም! በአባወራ ንቅናቄያችን የሚያላዝን፣ የሚነፋረቅን የሚያባብልም መንገድ አንከተልም። ይህ የወገን፣ የሀገር፣ የትውልድና የቤተክርስትያን ከአላውያን ይልቅ በእናት ጡት ነካሽ ሆዳደሮች መበዝበዝ፣ መቦጥቦጥ፣ መጎስቆልም ቁጭት ያደረባቸው ወንዶች ጉዞ ነውና፤ ቆፍጠን፣ ፈጠን፣ ነቃ ያለ ጀግና ትውልድ ይወጣው ዘንድ እናሳየዋለን እንጂ!

በፍኖተ-አባወራ እሁድ እንገናኛለን!
ይህ የአባቶቻችንን የመሰለ ነገር ግን ዘመናችንን የዋጀ ዐዲስ የጀግኖች ንቅናቄ ነው!

እኛ የአባቶቻችንን የአባታችንም ልጆች ነን!💪

አባወራ

20 Dec, 17:41


ጾታዊ ሚናን የሚክዱት ማርክሳዊ አውራ አልባ ማኅበረሰቦች
======================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ይህ ነገ መመሪያ ብቻ ኾኖ፣ በሥልጠና ተወስኖ የማይቀር፣ ፖሊሲ ኾኖ የሚወጣ ወንዱን ለማኮላሸት፣ ወኔውን ለመስለብ፣ ታቅዶበት የሚሠራ ኮሚኒስታዊ ሸፍጥ ነው።

የአውራ አምባ ማኅበረሰብ እኔ አውራ አልባ የምለው በአንድ ያልተማረ፣ በቅጡ የሚያስበውን እንኳ መናገር ያልቻለ ዙምራ የተባለ የዚያን ጊዜው ሕጻን የአሁኑ አዛውንት ተመሠረተ ሲሏችሁ እውነት አይምሰላችሁ።

ልክ እንደ አሁኑ በኢኦተቤ ልማትና ክርስትያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን እና በሮሚና ኢስትራቲ የድልድል ፕሮጀከት እንዲሁም በግበረ አበሮቿ በተመራ ትግራይ ላይ ተጠንቶ አማራ ክልል ላይ እንዲሰጥ በተወሰነው ሥልጠና ያለ ነው።

የአውራምባ ማኅበረሰብ በ1960ዎቹ አካባቢ ሲያቆጠቁጥ እነማን ነበሩ አይዞህ ባዮቹ? እነማንስ ስሙን ተውሰው በመገናኛ ብዙኃን አስተዋወቁት? አውራምባ ሲባል በ1990ዎቹ ምንና ማን ትዝ ይላችኋል?

ዛሬስ የሶሻሊስት አድናቂዎች አይደሉምን ወደ አደባባይ እንዲወጣ ዓለምአቀፍ እውቅናም እንዲያገኝ ያደረጉት? ለምን? ሀገር በቀል ስለኾነ ወይንስ እንደ ነቀርሳ (cancer) የተጣባቸውና ክርስትናም ቢቀበሉ እንኳ አለቅ ካላቸው ማርክሳዊ ሶሻሊስት ጽንሰ-ኃሳባቸው የተነሳ እንጂ !

ሀገር በቀል ነው ሲሏችሁ ዝም ብላችሁ አትቀበሉ! መርምሩ እንጂ! ይህ እኮ ካርል ማርክስ የጻፈውና ወንዳዊ፣ አባወራዊ፣ አርበኛዊ(patriotic) የኾነን ማኅበረሰብ ለማፍረስ የተጠነሰሰ መርዝ እንጂ!

ይኸው እነርሱም የጾታ እኩልነትን የጾታን ሚና ሽረን የተገኘን ቀደምት፣ ሀገር በቀል እውቀት ያለን ነን እያሉ ነው። እንዲሁም ናቸው ተብለው ተመዝግበዋል።

ማነው ከሮሚና እስትራቲ ጋር ሀገር በቀል እውቀትን አስፋፋለሁ ያለው? እርሷም decolonizing ስትል ሀገር በቀል እውቀትን ተጠቅሜ .....ለጊዜው ጾታዊ ጥቃትን የሚያስከትለውን ጾታዊ ሚና፣ ኋላ ግን ጾታዊ ሚናንም የሚያስገኝ ጾታን ራሱ ...

ለማንኛውም የተጣደልን ብዙ ነው!

🌟 ትተኛላችሁ ግን?
🌟 እውነት ድብን ያለ እንቅልፍስ ይወስዳችኋልን?
🌟 እስክትጠግቡስ መብላት ትችላላችሁን?
🌟 ፈታ ዘና እንበል" ብላችሁስ ትውላላችሁን?
🌟 ሰውነታችሁስ ፍዝዝ ድክም ይልባችኋልን?

እኔስ ከላይ የዘረዘርኳቸው አንዳቸውም አይደርሱብኝም! ይህንን ሁሉ ሥራ አስቀምጬ፤ ደሜ እንደሞላ፣ እጄ እንደፈጠነ፣ ብዕሬ እንደፈሰሰ፣ ሰውነት-ጸጉሬም እንደቆመ (alert) መሽቶ ይነጋል!

ብዙ የማገኛቸውና የማገናኛቸው የሚገናኙም መረጃዎች አሉኝ። ብዙዎቻችሁ ግን ቶሎ ትሰለቻላችሁ። ተግባራዊ ሥራም ከመሥራት ይልቅ ወሬን ማንሸራሸሩን ይዛችሁ ቀራችሁ። መሬት ላይ ያለውን ሥራ ማን ሊሠራላችሁ ነው ታዲያ!

ወንድሞቼ! "መኸሩ ብዙ ነው! ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው። እንግዲህ የመከሩን ጌታ ሠራተኞችን ወደ መኸሩ እንዲልክ ለምኑት..." ማቴ ፱ ፴፯-፴፰

ከታች የምታዩት የአውራ አልባው ማኅበረሰብ ጾታን ተገን አድርጎ ከእኩልነት በታች ሊያደርጋቸው የነበረን "የኋላቀር ማኅበረሰብ ፍረጃን እርሱም ጾታዊ ሚናን" ወንዶቹን እህል በማስበጠር ድባቅ ሲመቱት ያሳያል። ህም!

አባወራ

20 Dec, 11:09


ዛሬ ጾታዊ ሚና ነገ ጾታ ራሱ የለም ልጆቻችሁን ታደጉ
==================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

እንግሊዛውያንን ትናንት ይህ በሽታ ሲጀማምራቸው እንዲህ ነቀርሳ ኾኖ ትውልዳቸውን እንደሚያሳጣ፣ ቤተክርስትያንና ጳጳሳቱን ቅጥ የሚያሳጣ አልመሰላቸውም ነበር።

እውነት የኾነ እውቀት ይሞገታል፣ ቢሞገትም ተሸንፎ ይወድቃል ብለውም ጨርሰው አልጠበቁም ነበርና፤ በተዘጋጀላቸው ወጥመድ ተይዘው፣ ድጡ ላይ ተዘናግተው ከማጡ ሰምጠው ዛሬ መንፈራገጣቸው ሁሉ ከማጡ ጥልቅ የሚያዘቅጣቸው ኾነ!

ነግ በእኛ! ስትል አንብብ!

ዛሬ ቤተክርስትያን ከቅዱሳት መጻሕፍት፣ ከኦርቶዶክሳዊ ትውፊት፣ ከኢትዮጵያዊ ባህልም ባፈነገጠ መልኩ ካህናትን ጾታዊ ሚና ማለት የማኅበረሰቡ ፍረጃ እንጂ በተፈጥሮ ከሴትና ከወንድነት ኩነት የተነሳ የሚገኝ እንዳልኾነ ካስተማረች፤

ነገ በዚችው ቤተክርስትያን ጾታ ራሱ ሰው ሠራሽ፣ ማኅበረሰብ አመጣሽ፣ አንባገነናዊው አባታዊ ሥርዓትን አወዳሽ ብያኔ ወይንም ፍረጃ እንጂ ተፈጥሮአዊ እውነት፣ የተገለጠ ሐቅ አይደለም ብላ ታስተምራለች።

እንግሊዛውያን ዛሬ በቁጭት የሚያቃጥላቸው፣ የሚያብከነክናቸው ነገር ትናንት እዚህ ይደርሳል ያላሉት ግን በቸልተኝነት ያለፉት ይህንኑ ነው።

እርሱም ጾታዊ ሚና ማኅበረሰብ፣ በተለይም ያ"ጨቋኙና አንባገነኑ" ወንዳዊ አባታዊ ሥርዓት የፈጠረው እንጂ የተፈጥሮ እውነታ፣ የባህል ይኹንታ፣ ኖሮት በቅዱሳት መጻሕፍትም የሚደገፍ አይደለም ሲሏቸው ልክ ነው ብለው ነበር።

ዛሬ ሕጻናት ልጆቻቸው ጾታዊ ሚና አይደለም "ጾታ የለም" ብለው ከታች እንደምታዩት ወንዱ ሴት መኾን ሲፈልግ እንኳ አይኾንም ማለት የማይችሉ፤ እንቢታቸውም የሚያስከስስ የሚያሳስር ቢኾን መቃጠልና ማረር ብቻ ኾኗል እጣ ክፍላቸው!

C.S. Lewis የተባለው የዘመናችን እንግሊዛዊ ፈላስፋና የአንገሊካን ቤተክርስትያኗ የሥነ-መለኮት ተመራማሪ ይህ እንደሚመጣ ታውቆት "The Abolishin of Man" በሚል ርዕስ ያሳተመውን መጽሐፍ ወይንም ጭብጡን ፈልጋችሁ አንብቡት።

መጽሐፉ ትንሽ ገጽ ጥልቅ አስተውሎትን የሚጠይቁ ዕይታዎች ወይንም ትንቢታዊ ሂሶች የታጨቀ ነው።

እነዚያ ትንቢታዊ ዕይታዎች እርሱ እንደፈራቸው ዛሬ እየተገለጡ ነው። እጅግ የሚደንቀው ደግሞ እውነት፣ እውነት የኾነ እውቀት ሊነገርባቸው የሚገባቸው የትምህርት ተቋማት በተለይም መንፈሳዊ መካነ-አእምሮዎች የዚህ ሰለባ ሲኾኑ እያየን መምጣታችን ነው።

ሲ. ኤስ. ሊውስ መጪው ትውልድ በእውነት ዙሪያ አንድም እውነት በኾኑ እውቀቶች ላይ፣ አንድም በብዙኃን ዘንድ ተቀባይነት ያላቸው ባህላዊ፣ ሥነ-ምግባራዊ እሴቶች እየተካዱ ኢፍትሐዊና መከረኛ ዐለምን ይፈጥራሉ ይላል።

ልጆችንም ከልጅነታቸው ጀምረው እውነትን፣ እውነተኛ እውቀትን፣ ጽድቅን፣ ፍትሕን፣ ቅንነትን፣ ጀግንነትን ተፈጥሮአዊ እውቀትን ከማስተማር ይልቅ፤

ይህንንም መመርመር የሚችለውን አእምሮ ከመሳል (ከመሞረድ) ይልቅ እውነት የተባለውን ሁሉ ማኅበራዊ፣ ግለሰባዊ፣ አንጻራዊ ሥሪት እንጂ ዐለም የምትገዛበት ኩላዊ እውነት (Universal Truth or Objective Truth) የለም ብለው ያስተምሯቸዋል ብሎ ትዝብቱን ያስቀምጣል።

ካህናት በየትኛው አግባብና ትንታኔ ነው ለንስሃ ልጆቻቸው ጾታዊ ሚና ማኅበረሰባዊ ፍረጃ ነው ብለው እንዲያስተምሩ የሚሠለጥኑት የሚያስተምሩትስ። ይህ ዛሬ የተጀመረ ክህደትና ቅጥፈትስ ነገ ጾታንም የለም ወደ'ሚል ቅጥፈት፣ ግለሰባዊ ድቀት፣ ማኅበረሰባዊ ውድቀትስ አያመራምን?

ሲ. ኤስ. ሊውስ ለእንግሊዛውያን የራሳቸው ሰው ኾኖ ሳለ አስቀድሞ፣ አስጠንቅቆ፣ ነገራቸው አልሰሙትም፤ ሊሰሙትም ፈቃደኛ አልነበሩምና።

(ስለመጽሐፉ ጭብጥ የጻፈ አንዱ ተቆርቋሪ ይህንን ዛሬ የኾነባቸውን ቁልጭ አድርጎ የተናገረ መጽሐፍ እንደማይረባ ዕቃ ከመንገድ ላይ በሀያ አምስት ሳንቲም መግዛቱን በቁጭት ይናገራል)

ይኸው ዛሬ ሕጻናት ወንዶቻቸው ጾታ የለም በሚለው ነቀርሳ ተበክለው ከሕጻንነታቸው ጀምረው ይጠፋሉ። መንግሥትም ወሸላቸውን በመቁረጥና የእድገ-ንጥራቸው መመረት የሚያግድ መርዝ በመውጋት ያበረታታቸዋል።

ወላጅ እንኳ ልጆቼ ናቸው ብሎ መታደግ እስካይችል ድረስ፤ በሕግ ሥልጣኑ ተገፎ ይከለከላል። ትርፉ እህህ ብሎ መብከንከን ብቻ ኾኖባቸዋል!

በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረው ሰው፣
የሥላሴ ሕንጻ የኾነው ሰው፣
በእጁ አበጅቶ ነፍስ የዘራበት ሰው፣
ቢጠፋ ልጁን ልኮ በፍቅር የታደገውን ሰው፣
.
.
.

ዛሬ ራሱ በፈጠረው ነቀርሳ አስተሳሰብ እርሱም እውነት አንጻራዊ አንድም ማኅበራዊ ሥሪት እንጂ ሁሉን ገዢ እውነት አይደለም ሲል ከአባታቸው በአደራ የተሰጡትን ልጆች፣ በጎች፣ መንጎች፣ ትውልዶች እያጠፋ ይገኛል።

ሰምታችኋል!
ዝምታችሁ ክፋትን መተባበር እንዳይኾን ተጠንቀቁ!
በሰማችሁት እውነት ጽድቅ ልትሠሩበት ሲገባ ዝም ብላችሁ ትውልድ ወደ ጥፋቱ በመጣደፉ ኋላ እንዳትጠየቁ አስተውሉ!

ልብ-አልባ ወንዶች አትኹኑ! (Men Without Chest እንዲል ሊውስ)

እኛም ወንድ ከወንድም አባወራ ትኾኑ ዘንድ ጠራናችሁ!💪

ይህ ከታች የምታዩት ወንድ ልጅ ነገ የእኔና ያንተ ወንድ ልጅ እንዳይኾን ዛሬን እንሥራ። ጾታ የለም ብሎ እንዳይክድ፦ ጾታ አይደለም፤ ጾታዊ ሚናም እውነት እንደኾነና እንዳለ እናስተምር!

አባወራ

07 Dec, 05:15


እነ ተቋም አምላኩ! ይህንን ለሀገርና ለልጆች የሚደረግ ርብርብ ተከታተሉ!

አባወራ

07 Dec, 05:00


https://youtu.be/M8B1q1p-D4c?si=1oc_qOEnWyoq7dav

አባወራ

06 Dec, 08:19


ፍኖተ-አባወራ ሥልጠናችን ወንዶቻችንን ይጣራል
==============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ሰው ማለት ሰው የኾነ ነው ሰው የጠፋለት! እንዲሉ ወንድ ማለትም ወንድ የኾነ ነው ወንድ የጠፋለት! አንድም ወንድ ማለት አባወራ የኾነ ነው አልጫ በበዛበት ብለንም ልናመጣው እንችላለን!

የፍኖተ-አባወራ ሥልጠናችን እነኾ ወንዶቻችንን ይጣራል። ለዘመናት አሰስነትን አጽድቀው፣ አልጫነት መንፈሳዊነት ብለው፣ ምስኪንነትንም ዘመናዊነት አድርገው ከጋቱን፦ አልጫ፣ ምስኪን፣ ሆዳደርና ሽልጥለጥ ትውልድ ካፈራብን ስሑት አስተሳሰብ የምንላቀቅበት ነው።

ወደዚህ ሥልጠና የምትመጡት ብሶት ለማጋራት፣ ምሬት ለማውራት፣ ጥላቻን ለመዝራት አይደለም። ነገር ግን ለቤተሰባችን፣ ለማኅበረሰባችን፣ ለቤተክርስተያናችንና ለሀገራችንም ውድቀት ተጠያቂ የኾንነው እኛ ወንዶቹ መኾናችንን እንድናውቅ ነው።

ማወቅ ብቻም አይበቃም! ይልቁንስ ከተፈጥሮኣዊ ባሕርያችን ከልዕልናው ከወደቅንበት፦ ኃላፊነት ከማይፈጽም ግዳጅም ከማይወጣ ጠባያችን ለመነሳትና የቀደሙትንም ለማንሳት እንጂ!

ወንድምዓለም! ልብ አድርግ አባትህ በሰጠህ ጸጋ፣ በመልክና በዓይነት ባስቀመጠልህም መክሊት በልጽገህ የመጣህለትን ዓላማ እንድትፈጽም ይፈልጋል፤ ይጠይቅሃልም!

አባትህ መራራውን ዐለም እውነትን ይዘህ፣ ጽድቅን ፈጽመህ፣ ፍትህንም አስፍነህ ታጣፍጥበት ዘንድ የሰጠህን ጨው-መክሊትህን፣ ወንድነት ጸጋህን እንዳትሠለጥንበትና፣ እንዳትበለጽግበትም የሚፈልገው ጠላትህ ሲኾን ካለማወቅ ግን ጥቂት ወዳጆችህ ይኾናሉ።

ታናሼ! ማዘን፣ ማላዘን፣ ማልቀስ፣ መነፋረቅ ጠባይህ አይኹን! ዘወትር ብሶት፣ ሮሮ፣ ከሚናገሩት ከሚጽፉትም ተለይ!

ይልቁንስ ራስክን ከወደቅክበት የሥነ-ልቦና ጉስቁልና አንሳና ያጎነበሰች ሀገርክን፣ ቤተክርስትያንክን፣ ማኅበረሰብክን፣ ቤተሰብክን፣ ልጆችክን፣ ትዳርክንም ቀና አድርጋቸው!

ዐይኖቻቸው አንተን ተስፋ ሲያደርጉ፣ ልትጠብቃቸው፣ ልትሟገትላቸው፣ መልካሙን ልታቆይላቸውም ሲገባ ወዴት ትሸሻለህ፤ ትቀራለህስ!

ራስክን እሁድ እሁድ ታህሳስ 06-27 2017 ዓ.ም. ለሚኖረው ሥልጠና አዘጋጅ!
ለበለጠ መረጃም +251911674687 ደውል፣ ጻፍ..

እየጠብቅሃለሁ!💪

አባወራ

05 Dec, 13:12


https://youtu.be/f64UqbwqXUk?si=apk2E89jQemsh4qE

አባወራ

05 Dec, 09:19


የሥልጠና መመሪያ መጽሐፍ ፪
===================
ይኸው ካላነበብነው ላላችሁ! የቀለም ምልክቶቹ የእኔ ናቸው። መጻሕፍቱን photo አነሳቸዋለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር።

አባወራ

05 Dec, 09:17


የሥልጠና መመሪያ መጽሐፍ ፩
================
ይኸው ካላነበብነው ላላችሁ! የቀለም ምልክቶቹ የእኔ ናቸው። መጻሕፍቱን photo አነሳቸዋለሁ ብዬ አላሰብኩም ነበር።

አባወራ

05 Dec, 05:40


እህትዓለም! ይህንን ስሚው!
https://youtu.be/lcuJfu1jItk?si=Dp3OaxrFDuqmkxtp

አባወራ

05 Dec, 04:25


እህቶቻችንን ብሶት ማስተማር ጽድቅን አይሠራም
===============================

አንቺ የውብ ዳር!

አንድ ወንድምሽ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ በልምድም በስሎ ያተረፋቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሻል፤ አንቺ ግን በወደድሽው ኑሪ!

ትውልዱን የተጎዳውንም ያለተጎዳውንም፣ በቃላት እያዋዙ፣ በትርክት እያዛሉ፣ በናላው እየሳሉ ብሶተኛ አድርጎ ማስተማር በባርነት ሊገዛው ለሚናፍቀው ጠላት ኹነኛ መንገድ ነው።

አንድም ደግሞ እንዲህ ያለውን ትርክት ደጋግሞ ለወገናቸው እየነገሩ የራሳቸውን ትውልድ ማለጭ ላልጫና ሆዳደር ምንደኞች ከቀደመው ጠላት ቀለብ የሚያሰፍሩበት ወጭታቸው ነው።

ኾኖም ግን ይኸው መሰሪና ሸፍጠኛ መንገድ በእውነት ሊጋለጥ ሲገባና ያንንም እውነት ሊነግሩን፣ ቀድመውን ኖረውም ሊያሳዩን በሚገባቸው መንፈሳዊ መሪዎች ዘንድም ተግባራዊ ሲኾን ግን ከፍተኛ ጥንቃቄ፣ ትኩረትና መፍትሔ ይፈልጋል።

ምክንያቱም እነርሱ የትውልዱ መሪ፣ የድኅነቱን መንገድ ጠቋሚ፣ የሚጠቅመውንም መካሪ ተደርገው ይቆጠራሉና የጥፋት መጠናቸው ያይላል።

እህትዓለም! በቤተክርስትያናችን የመጣብን፣ በእረኞቻችን የተቃጣብን ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን ቤተሰብ ግንባታ፣ ጥንካሬና ብልጽግናም ታቅዶ የመጣው ትምህርት ለአንቺና መሰል እህቶቼ ብሶትን ከዐለም ቀድተው ለሚያስተምሩበት ነው።

ብሶተኛ ኾኖ የወጣ ትውልድ በሕይወቱ ለሚኾነው በተለይም ለሚጎዳበት አንድም ነገር ኃላፊነት መውሰድ አይፈልግም። ይልቁንስ እንትናና እንቶኔ ይህን አስበው፣ እንዲህ ተናግረው እንዲያም አደረጉብኝ ሲል ያማርራል እንጂ።

በሕይወታችን ለሚኾነው፣ ኃላፊነት ባልወሰድንበትና ልንወስድበትም ባልፈለግነው ልክ ደግሞ ደስታ ማጣታችንም እንዲሁ ይኾናል።

ይህን ርዕሰ ጉዳይ ከወዳጄ አብርሃም ጋር በሰፊው ዳሰነዋል። ጠባቧ ደጅ ላይ ይጠብቁን። እግረ መንገዳችሁን ደግሞ መጻሕፍቱ እንዳይሰራጩና ሥልጠናው እንዳይሰጥ ፈርሙ!👇

https://chng.it/BGPB2rr4yT

አባወራ

04 Dec, 07:48


አጀንዳ ሳይኖረው አጀንዳዬን አታስጥለኝ ይለኛል
========================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ማኅበራዊ ትስስር ገጾች(ማትገጽ) በአካል ከተወዘትንበት ጎሬ ሳንወጣ በድድድ ማስጫው የበይነመረብ አደባባይ ላይ ወሬ የምናሰጣበትና የምናስጣጣበት መኾኑ እርግጥ ነው።

ላወቀበትና ለተጠቀመበት ግን ምንም የተሰወረ ነገር እንደሌለ ሊደበቅም የሚችል እንደማይኖር ላስተዋለበት ግን ብዙ ራሱን የሚገነባበትና የሚያተርፍበት ነገር ይገበይበታል።

ይኹን እንጂ በአያሌው ባካኝ፣ ዓላማ ቢስ፣ ከንቱ ትውልድ ማፍራታቸው ግን ጥቅማቸውን የጋረደ ትርፋቸውን የቀበረ፣ ጉዳታቸውንም ያጎላ ጉዳይ ኾኗል።

ምን ያክሎቻችሁ በአንድ ርዕሰ ጉዳይ ላይ እና እርሱን መጋቢ ወይንም ተመጋጋቢ የኾኑ ንዑስ ጉዳዮችን ይዘው፤ በዚያ መስክ ጥናት፣ ምርምር፣ ውይይት፣ ሙግት አድርገው፤ ትውልድን ለመገንባት፣ ዐለምን ለፍጥረቱ ምቹ ስፍራ በማድረጉ ሂደት ጥረት የሚያደርጉ ግለሰቦችን ወይንም ተቋማትን ታውቃላችሁ።

የማትገጾቻችን አንዱ ጉዳት እርሱ ነው። ይኸውም ተጠቃሚውን የተለያዩ፣ ትኩረት የሚፈልጉ፣ ነገር ግን ደግሞ ራሳቸውን ችለው ሊሠሩ በሚገባቸው ጥልቅ በኾኑ ርዕሶች ላይ፣ ንዑሳን ርዕሶችም መካከል እንዲባክን የማድረግ ስህበታቸው ነው።

በእንደዚህ ዓይነቱ እዛና እዚህ በረገጠ አጀንዳ ደግሞ ትውልድ አይገነባም። የመረጃ ቅንጥብጣቢ ይዞ በመሮጥ፣ ቀድሞ በመጮህ፣ በእነርሱም ተከታይ ማፍራትን ስኬት አድርገው የሚቆጥሩ አውርቶ አደሮችን እናፈራለንና።

በአውርቶ አደሮች ደግሞ የሚፈርስ ቢኖር እንጂ የሚገነባ ሀገር እንደሌለ ከታሪክ መማር ይገባናል። የምናወራው ምን ልክና ተገቢ ቢኾንም ቅሉ በዐለም ያለው ፈተና ተጋፍጦና ተጋፍቶ በተግባር የሚገነባ ደፋር እስካልመጣ ድረስ በገጠመን ፈተና ስናዝንና ስናላዝን መኖራችን እርግጥ ይኾናል።

ያላችሁባቸውን የማትገጾች እስቲ አስተውሉ! ስለምን፣ እንዴት፣ ለምን፣ እስከመቼስ ታወራላችሁ? እኔ ካሉት በርካታ የማትገጾች በጣም ጥቂቱን በቁጥር ሁለት እከታተላለሁ። ምክንያቱም አብዛኛው ለመሥራት በጨከነና በቆረጠ ሳይኾን በሚያዝንና በሚያላዝን አልጫ አስተያየት ስለሚሞላ።

ከመበሳጨትህ በፊት ቆምብለህ አስተውል!

"የመረጃ ምንጮቻችን ናቸው፣ ሕዝቡን ያነቁታል፣ እነርሱን የሰጠን እግዚአብሄር ይመስገን...." ትላለህ እንጂ ከሰማህ በኋላ ምን አደረክ? እነርሱስ መረጃ ከሰጡህ በኋላ መፍትሔ ጠቁመዋል፣ የመፍትሔውስ አካል ለመኾን ፈቅደዋል፣ በሂደቱስ መስዋዕት ለመኾን ጨክነዋል፣ ዐይተሃቸዋልስ?

ዐየህ ፈተናችንን ከሚያከፉት ነገሮች ውስጥ፦
፩ኛውና ዋነኛው ትውልድን የምንገነባበት እውነት የኾነ እውቀት አጀንዳችንን ይዘን ከመሰማራት ይልቅ ከጠላትም በለው ከወዳጅ የሚጣልንን ቅንጥብጣቢ አጀንዳ ይዘን መሮጣችን ነው።

፪ኛው ደግሞ እርሱንም ይዘን መፍትሔ ማቅረብና የመፍትሔው ተሳታፊ፣ ለመከራው ፊት ተሰላፊ ከመኾን ይልቅ አንዲት ጥግ ይዘን እንደ ፈሪ ውሻ መጮሃችን ነው።

፫ኛውና የዛሬው ርዕሰ-ጉዳዬ ግን እኛ ያነሳነው አጀንዳ ብቸኛው፣ ኹነኛው፣ አንገብጋቢውና፣ ለሁሉም ችግሮች የተሟላ መፍትሔ የሚኾን አድርገን ሌሎች አጀንዳዎችን ለመስማት አለመፈለጋችን ነው።

ሰሞኑን በቤተክርስያንና በማኅበረ ምዕመኗ ላይተጋርጧል ብዬ በምጽፈው አደገኛ ጉዳይ፦

፩ ከማትገጽ ያገኙትን አጀንዳ አጀንዳዬ የሚሉ፣
፪ መፍትሔ ቢጢ ከመወርወር ውጪ መጋጠሚያ ሜዳው ላይ የማይወጡ፣
፫ አጀንዳ-አልባ ኾነው ሳለ "አጀንዳዬን ታናጥብብኛለህ" የሚሉ ገጠሙኝ!

ወንድምዓለም! ታስታውሰው ከኾነ ቤተክርስትያን ጠፍቶ የተገኘ፣ ወጥቶ የተመለሰም አንድ ልጅ ነበራት እርሱባለው በለጠ የሚባል።

በዘጠናዎቹ መጨረሻ አካባቢ እርሱ ገብቶበት ከነበረው ማጥ ውስጥ የሰማውንና በማስረጃ የደረሰበትን ኢኦተቤን ላይ የተነጣጠረ ዘመቻ ቤተክርስተያኗ ውስጥ ለነበሩ አሁንም ላሉ መምህራን በስንት ጭቅጭቅ አስረዳቸው!

ወቅቱ ደግሞ ምርጫ ዘጠና ሰባት ወቅት ነበርና የመንግሥት ለውጥ ይመጣል ተብሎ፣ የፖለቲካው ትኩሳት ሁሉም ላይ ንዳድ ፈጥሮ፣ ዐየሩንም ተቆጣጥሮት ነበር።

ይህንን ጊዜ እርሱ የታየውን ስጋት የነገራቸው አካላት (ግለሰቦች) ያነሳውን ችግር በቅጡም ሳይረዱ፣ ርዕሰጉዳዩም ያን ያክል አንገብጋቢ እንዳልኾነና ጊዜውም እንዳልደረሰ ፊት ነስተው መልሰውታል።

እርሱም የታየውን ሊያስረዳቸው የመረጣቸው፣ ይረዱኛል ያላቸው ግለሰቦች ሲገፉት በብዙ መከራ መጽሐፉን አሳትሞ፤ ስለ ሀገሩና ትውልድ ያሰበው፣ ያስጨነቀውም እረፍት እንደነሳው፤ በስጋዊ ድሎትና ምቾት (በሀገረ ካናዳ) ከቤተሰቦቹ ጋር መኖር እየቻለ ተንከራቶ፣ በኋላም ግዳጁን በሰጠው አባቱ በፈቀደው መንገድ ተጠርቶ ሄዷል።

እርሱ ካለፈ በኋላ እነዚያው ጠርቶ የነገራቸው መምህራን እያሉ ቤተክርስትያን አስቀድሞ በጠቀሰው እያንዳንዱ የመስቀል መንገድ የእርሷና ማኅበረ ምዕመናኑ መከራቸው ኾኗል!

እነርሱ "አንገብጋቢና ቀዳሚ ጉዳይ ነው" ባሉት ነገር እንኳ ቤተክርስተያን በምትጠቀምበት ጉዳይ ሊሳተፉ ይቅርና የበይ ተመልካች ኾነው ጭርሱንም ለዘመናት የሚተርፍ ፈተና ጥለውባት አሁንም እዚያው ይኖራሉ።

ሳተናው!
ከተሰጠን፣ ካለን፣ ከደረስንበትና እስክንደርስበትም ከተቀመጠልን ሁሉ ከእኛ የኾነ አንዳች የለም፦ ሁሉ የእግዚአብሄር አባታችን የእርሱንም ክብር የምንገልጥበት፣ የምስራቹን ወንጌል በወሬ አይደለም በኑሮ የምንመሰክርበት፣ ጽድቅ ሠርተን ፍትሕ አስፍነንም ሩጫችንን ጨርሰን ወደ እርሱ የምንሰበሰብበት ነው!

ተቀጥረን በምንሠራበት በእኛ ላይ የተሾመው አለቃ ሥራ የሚሰጠን ወይንም ሥራ የተቋረጠን ከፋያችን ግድ ከሚጠብቅብን ግዳጅ ይልቅ በራሳችን አስበን የምንሠራው፣ ጠዋት የሚቀሰቅሰን፣ ዕለት ዕለት የሚያሳስበን ጉዳይ አጀንዳም ሊኖረን ይገባል (አጀንዳ ሞልቷል "መኸሩ ብዙ ነው ሠራተኞች ግን ጥቂት ናቸው..." እንደተባለ)።

እንደ ሰው በተለይም ደግሞ እንደ ወንድ ይህ የምንኖርበት ንዴት(የሚነዳን)፣ የምንኖርለት ምክንያት፣ የመኖራችን ጥቅም፣ የሕይወታችንም ትርጉም የሚኾነን እርሱ ነው።

ታናሼ! ከማትገጽ የምትሰበስበው አጀንዳ መነሻ ምክንያትህ ኾኖ በቋሚነትና በዘላቂነት በንባብና በተግባራዊ ሕይወት እያዳበርክና እየመዘንክ የማትሠራው ጉዳይ ከኾነ ወሬ ቃራሚ እንጂ ራስክንም ኾነ ሌላውን የምትቀይርበት አጀንዳ የለህም!

በእርግጥ ገንዘብ፣ ዝና፣ ክብር፣ ስም፣ ውዳሴ አግኝተህበት ይኾናል! እነዚህ ሁሉ ግን የመጣችው ለእነርሱ እንዳልኾነ ለምታውቀው ነፍስህ እረፍት አይሰጧትም!

ወንድምዓለሜ! አጀንዳ-አልባ ኾነህ አትኑር! ከማትገጽ የምትቃርመውን፣ አንተም ነካክተህ የምታቀብለውንና የምታቀባብለው ቅጥ አንባሩ የጠፋ ወሬ "አጀንዳዬ" አትበልኝ። ይልቁንስ ጥናት ምርምር ሠርተህበት በሕይወትም ተገልጠህበት ዐለምን የምታጣፍጥበትን አጀንዳ ወጥን እንጂ!

አለበለዚያ ደግሞ አጀንዳ ይዘው፣ ያነበቡትን በተግባር ፈትነው፣ በስሌትና አመክንዮ መዝነው ከሚያስተምሩት ስር በትኅትና ተማር! የማይኖሩትን ጀብድ የሚኖሩትን አልጫነት ከሚያስተምሩት አስመሳዮች መጠበቅም ታላቅ ተጋድሎ ነው።

ቤተክርስትያን ባመጣችው እያሰራጨችና እያሠለጠነች ባለችው የሥርዓ-ጾታ ትምህርት፤ በባለድርሻ አካላትም በተዘረጉት መርሐግብሮች እጅግ አደገኛ መንገድ ላይ ነች!

አባወራ

03 Dec, 07:40


ወላድ-ወንዶችን መሐን-ሴቶችን የሚያፈሩ ማኅበራት
============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

☀️ ወላድ-ወንዶች ያልኳቸው፦
ተፈጥሮአዊ ሴትነት ባሕሪያቸውን የጋረደ ወንዳወንድነት ጠባይን የተላበሱ፣ በማርገዝና መውለዳቸው ብቻ ሴትነታቸው የሚገለጥና የሚረጋገጥ፣ ዛሬ ላይ ቤተክርስተያናችንና ማኅበራት ባፍና በመጣፍ ከተፈጥሮአቸውና ከፈጣሪያቸው እያራቋቸው ያሉትን ሴቶች ስጠቅስ ነው።

☀️ መሐን-ሴቶች ያልኳቸው፦
ተፈጥሮኣዊው ወንድነት ባሕርያቸውን ዐለም "ዘመናዊነትና መንፈሳዊነት ነው" ብላ ባለበሰቻቸው ሴታሴት ጠባይ የቀበሩ፣ ተኝተው ማስረገዝና ቆሞ መሽናት ብቻ ወንድነት የሚመስላቸው፣ በበዛው ጠባያቸው ሴታሴት የኾኑ ኾኖም ግን አርግዘው መውለድ የማይችሉ ቤተክርስተያንና ማኅበራት ባፍና በመጣፍ ከተፈጥሮኣቸውና ከፈጣሪያቸው እያራቋቸው ያሉትን ወንዶች ከአባወራዎቹ ስለይ ነው።

አሁን ባለንበት ጊዜና ዘመን በሀገራችን በተለይም ከዋና ከተማችን ዐዲስ አበባ ወደ ሌሎች ከተሞች እየተስፋፋ ያለው ክርስትናን ማለጭ በዚያውም ቤተሰብና ማኅበረሰብ ሀገርንም ሊታደግ ያለውን ትውልዱን ማለጭ ነው።

🌟 የአልጫን ትርጉም በእኛ ዐውደ-ንባብ (context) አስታውስ!

ቤተክርስትያናችን ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰ አደጋ እንደተጋረጠባት ለሁላችንም ግልጽ ነው። እንደ ተቋም በወንዶች በተለይም ለአገልግሎት በተጠሩ አባቶች፣ ምዕመናንን በለምለሙ የወንጌል መስክ እንዲያሰማሩ በተጠሩ እረኞች እንደመመራቷ ተቋሟ የደረሰባት ውድቀት በማኅበረሰባችን ውስጥ የተንሰራፋውን የወንዶች አሰስነት፣ አልጫነትም ኹነኛ ማሳያ ነው።

አልጫ ከኾነ ወንድ ተፈጥሮውን በተለይም ፈጣሪውን በእብሪት ከሞገተ፣ ከጣለና ከተወ ትውልድ ወልዶ ቢያሳድግ፣ አሳድጎም ምን ሃይማኖተኛ አድርጎ ልጆቹን ቢያወጣ ተፈጥሮውን የካደበት ነቀርሳን ለልጆቹ አውርሶ ነው።

ሀገራችን በሸፍጠኛው የሶሻሊዝም ወረርሺኝ ስትያዝና ልጆቿም በዚሁ በሽታ ሲለከፉ የኾነው ነገር ይኸው ነው፦ ከቤተመንግሥት እስከ ቤተክህነት ያለውን (ሁለቱ ሀገር በመገንባቱ ሂደት ከፍተኛ ሚና ያላቸው) ትውልዱን በተለይም ከትውልዱ የተማረ-እፍታውን በተፈጥሮውና በፈጣሪው ላይ አመጽን አስተማረ።

ይህ ነቀርሳ በዝቶና ተባዝቶ አሁን ለደረስንበት ዝቅጠትና ውርደት ሲያበቃን፦

👉 እንኳን ለሌሎች ለራሳቸው ያላወቁ፣
👉 አርአያነቱ ቀርቶ በሚያስተምሩት ትምህርት በቅጡ የማይኖሩ፣
👉 ማዕረግና ሽበት ተጭኗቸው ሆዳቸውም ጎትቷቸው ባፍጢማቸው የተደፉ መሪዎችን እረኞችንም አፈራን!

እነርሱም ዝናና ማዕረግ፣ ሹመትና ሽልማት፣ ገንዘብና ጥሪት የሚሹ የሚያሳድዱም ኾኑና ትውልዱን ተፈጥሮኣዊ ጸጋውን፣ አባቱ በአደራ ጽድቅ እንዲሠራበት የሰጠውን መክሊቱን ከማስተማር ይልቅ ለራሳቸው ምንደኝነት እንዲመቻቸው አሰስነቱን አጽድቀው የሚግቱት፣ አልጫነቱንም "መንፈሳዊነት" እያሉ የሚደልሉት ኾነዋል።

በዚህ ደላይ እና ሸፍጠኛ ትምህርታቸውም ፈጣሪ ወንድና ሴት አድርጎ የፈጠረውን ሰው፤

🌟 በወንድነታቸውና በሴትነታቸው ተዋደውና ተዋሕደው በአንድነት፣
🌟 ግን ደግሞ ሳይቀላቀልና ሳይደበላለቅ በተቀመጠ መክሊታቸው ለአንድ ዓላማ በተጠሩባቸው ሚናዎች በልዩነት መቀመጥ እንዳለባቸው አያስተምሯቸውም።

ይልቁንስ "ክርስትና ፍቅር ነው፣ ክርስቶስ ፍቅር ነው፣ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ፣ በክርስቶስ ወንድም ሴትም የለም...." እያሉ በማር በተለወሰ መርዛማ ትምህርታቸው ትውልዴን ይነድፉታል። በዚህም በርካቶች ተፈጥሮኣቸውን ጠልተው፣ ጥለውና ተጠይፈው ወደ አልጫነት፣ ጉስቁልና፣ እርኩሰትና ኃጢያት ተሰደዋል።

ወዮ ለእኛ!

ወንድምዓለም! ክርስትናችን በተለይም ደግሞ ቤተክርስተያንን ተገን አድርገው የተቋቋሙ ማኅበራት ከተፈጥሮቸው የተሰደዱ ሴቶችን ወላድ ወንዶች አድርገው እያከሰሯቸው ይገኛሉ!

ታናሼ! አሁን በተስፋፋው የክርስትና ትምህርት፣ የመርሐግብሩ አካሄድና ያመጣነው ባዕድ ልማድ እና ማኅበራቱም ከተፈጥሮኣቸው እጅግ የራቁ፣ የተለዩና የተጣሉ(ጠብ) ወንዶችን ማርገዝ መውለድ የማይችሉ፦ መሐን ሴቶች አድርገው እየሰጡን ይገኛሉ።

ከእነዚህ ሴታሴት ከኾኑ፣ መልክና አለባበስ ከሚያሳምሩ፣ ወንዳወንድነታቸው አሽቆልቁሎ ወለሉ ላይ ከተፈጠፈጠባቸው መሐን ሴቶች "ወንዶች"፦ ሚስቶቻቸው፣ ትውልድ፣ ቤተክርስያንና ሀገርም ከአላውያን ነገሥታት ይታደጉናል ብለው አይጠብቁም፤ ቢጠብቁም አያገኙም።

እንደውም አሳለፈው የሚሰጡን አልጫ ሆዳደሮች የመኾን እድላቸውን፦ የተፈጠፈጠ ወንዳወንድነታቸው፣ ያሽቆለቆለና የተኮላሸም ወንዴዘራቸው ያጠናክረዋል እንጂ!

የወጣላቸውንና የተዋጣላቸውን አልጫ ወንዶችን እያፈሩ ያሉት ማኅበራት ወንዶቹን መሐን-ሴቶች እያደረጉ ማውጣታቸውን ካላቆሙ ትውልዱ ለጾታው ግራ የገባው ሽልጥልጥ ወንድ እንደሚኾን አትጠራሩ!

እውነት ከኾነ እውቀት ይልቅ አንድም እውነትና ጽድቅ ሊሠሩበት ፍትሕም እንዲያሰፍኑበት ከተሰጣቸው መክሊት ተፈጥሮአችው ይልቅ ስሜታቸውን የሚያዳምጡ፣ በስሜት ተነሳስተው፣ በስሜት የሚነዱ፣ የሚነጉዱም ባለቃጭል ሰዎች፦ መሐን-ሴቶች ብንላቸው እንጂ ወንድ ብለን ለመጥራት ተፈጥሮአዊ ባሕርያቸውን ተጣብቶ የተገለጠባቸው የበዛ ሴታሴት ጠባያቸው ይከለክለናል።

ታናሼ! ሀገራችንን፣ ቤተክርስትያናችንን፣ ማኅበራቱንም ኾነ ማኅበረሰቡን የመታው፦ የመሪ-ራስ፣ የመልካም እረኛም ድርቅ፤ መነሻው እያንዳንዳችን፣ እኔና አንተ ያንን ሚና እንወጣበት ዘንድ የተሰጠንን መክሊት ወንድነታችንን መጣላችን ነው።

አሁንም የእነዚያን ተቋማት ሕልውና መታደግ የምትሻ ከኾነ ማዘን ማላዘን፣ መነፋረቁንና በሌሎች ላይ ጣት መቀሰሩን ተውና ሀገር ከነድንበራ፣ ቤተክርስተያን ከነሥርዓቷ... አባቶችህ ያቆዩበትን፣ የናቅከውን ተፈጥሮ ወንድነት መክሊትህን ዐድስ።

እኛስ አልጫነትን ተጠይፈው፣ ከሰበበኛነት ርቀው፣ ስንፍናን አስወግደው፣ በስሜቶቻቸው ላይ የሚሠለጥኑ ጽድቅም የሚሠሩበትን አባወራዎች እናሠለጥናለን!

ሰበበኛ፣ አላዛኝና ነፍራቃ ከሚያደርጉህ ጉባኤዎች ተለይተህ ና! በማላዘንና በማማረር፣ "በመሬት አንቀጥቅጥ" መዝሙራቸውም ልብህን በመስለብ፦ መሐን-ሴት፣ ሽልጥልጥ ወንድ፣ ባርነት የሚስማማው አልጫ ያደርጉሃልና!

"ማን መንገዱን ዐሳየኝ መራኝም" እንዳትል ይኸው ተጽፏል! አንብበኸዋልም! ውርድ ከራሴ!

እጠብቅሃለሁ!💪

አባወራ

01 Dec, 03:37


https://youtu.be/uOESQZRijRs?si=44i5U-e4JYSBBpHJ

አባወራ

30 Nov, 04:16


https://youtu.be/u3loyalHaEQ?si=lLuTwyl2-DcbzTqX

አባወራ

29 Nov, 14:29


በነገርከኝ ቃል ቅደመኝ
==============
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ወንድምዓለም! የምትነግረኝ "እውነት"፤ እውነት ትውልድ የሚድንበት "እውነት" ከኾነ በእርሱ ተገልጠህ አይለህም ቅደመኝ። አንተ የምትነግረኝን መድኃኒት ያልከውን "እውነት" የማትነካው ወይንም ደግሞ ምሬቱ የማይደርስብህ፣ ብትፈለግ ከማትገኝበት ጥግ ኾነህ እኔን ከኋላ አትንዳኝ!

እውነተኛ እረኛ፣ መሪም ከፊት ቀድሞ በጎቹን ይጣራል! ጠላት፣ ነጣቂ ተኩላ ቢመጣም ይተናነቃል፤ ከገደል ቢደርሱ ይመልሳል እንጂ ከመንጋው መሐል አልያም ከኋላ ኾኖ መንጋው የሚደርስበትንና የደረሰበትን ከማያይበት ከማይደርስበትም ኋላ ርቆ ጅራፍ ጩኸቱን አያበዛም!

ከእኔ ትድግና የምትጠብቅ እንደዚያም እንድገለጥ የምትጨቀጭቀኝ አንተ፤ ለትድግና በሚያስፈልገው መክሊት፦ ድፍረት፣ ጥንካሬ፣ ሥልጣኔና ኃይለኝነትም ኾነ ጭካኔ አንተው ቀድመህ በልጽገህበትም ስትሄድበት ልይህ!

የማትኖረውን፣ ያልሞከርከውን፣ ልትነካው የማትፈልገውን ታሪክ እየጠቀስክ የምትጮህብኝ ወንድሜ እባክህን በጣም ስረዳህ እንዳንተው ጯኺ፣ የዩቲዩብና የመጣፍ ሸቃላ ብኾን እንጂ ራሴን ሠርቼበት ለትድግና አልበቃበትምና አታደንቁረኝ!

አልጫ አድረገህ አሳድገኸኝ፦ ትዳር ቤተሰብክን፣ ማኅበረሰብ ሀገርክን፣ ቤተክርስትያንንና ትውፊትክን እንዴት አትታደግም እንዴት ዝም ትላለህ፤ አትበለኝ! የነገርከኝም ኾነ ያሳየኸኝ "ጽድቅ የሚገኝበትን" አልጫነት ነውና!

ወንድምዓለሜ! እውነት በኾነው እውቀት ተሠርቼ በወንድነት መክሊቴ ትድግናን እፈጽም ዘንድ፦ በነገርከኝ፣ በምትነግረኝም ቃል በጀግንነቱ በተግባር ቅደመኝ፣ ዐሳየኝም እንጂ!

ይህንን የምታነበው አንተ! አስቀድመህ ትድግናን ትፈጽምበት ዘንድ የተሰጠህን ወንድነትክን እወቀው ሠልጥንበት በልጽግበትም።

ሲቀጥል ግን እርሱንም ደግሞ ከምታወራኝ ከምትመክረኝ ይልቅ ቀድመህ ዐሳየኝ! በወንዶች ዐለም፣ በጀግንነት ተነስቶ በመስዕዋትነት በሚጠናቀቀው አገልግሎት ብዙ ማውራት ጀግናን አይወልድም፤ ከሚያወቋት ጥቂቷን በመኖር በተግባር በመግለጥ እንጂ!

ወንድምዓለም! ዛሬ የማኅበራዊ ትስስር ገጾቹ ትውልዱን ወሬኛ አድርገውታል። ሁሉ መፍትሔ አለኝ ባይ ነው! እርሷኑ ግን ጠዋትና ማታ ከምግብ በፊትና በኋላ እያለ ያዛታል እንጂ እርሱ ጨክኖ አይውጣትም!

በሌላ አገላለጽ፦ የምትነግረኝን አማራጭ መንገድ ቀድመኸኝ ከፊቴ፣ ጨክነህ በሞቴ፣ ሳትተወኝ ለፍርሃቴ አሳየኝ! ምሳሌ ኹነኝ!

ይኹን እንጂ ብዙ አውሪዎች ከበቡኝ፤ ሠሪውንም ጋረዱኝ እኔንም ወሬኛ አውርቶ አደር ሊያደርጉኝ፤ ሆዳደሮች አውርተው ያድራሉና ከእነርሱ ሊደምሩኝ!

ሁሉ አውሪ ኾነ! በዚህ ላይ ማውራቱ ብቻ ሲያስከፍለው ጊዜ የሚጠቅመውንም፣ የማይጠቅመውንም፣ የሚጎዳውንም ጭምር እያወራ ሸቃላ ኾነ እንጂ

ይህ ደግሞ አስቀድመው ኾነም ብለው ትውልዱ አልጫ እንዲኾን አሰስነትን አጽድቀው ለሚግቱት ሆዳደሮች ለትምህርታቸው ኹነኛ ምሳሌ መኾን ነው።

ስለኾነም ወዳጄ በምትነግረኝ እውነት ቅደመኝ! ኖረህ ዐሳየኝ! መከራ ተቀብለህበት አስከትለኝ! አለበለዚያ ግን የማይኖሩትን ጀግንነት አርቀው ኮንነውም፣ የሚኖሩትን አልጫነት አቅርበው አጽድቀውም የሚጮኹ ሸቃላዎችን አትኹንብኝ!

እነርሱ አድክመውኛልና! አንድም እንደ እነርሱ ትድግናን ጠባቂ፣ መታደግን ፈሪ፣ ስለ ትደግና አሰላሳይና ተንታኝ አውሪም ታደርገኛለህና!

ወንድምዓለም! ብዙ ካወራኸኝ ጀግንነት ጥቂት ኖረህበት፣ መከራንም ስትቀበልበት ልይ! የነፃነትን ክፍያ ትክክለኛዋንም ዋጋ ግለጥልኝ! በነገርከኝ፣ ባስተማርከኝ ቃል ቅደመኝ!

(ኑሮ ያንገላታውን ትውልድ በማይኖሩት ጀግንነት በሚያስገመግም ጩኸት ሲያደክሙት ብታዘብ)

አባወራ

29 Nov, 03:07


ካሳደጉት አልጫ ትድግናን አይጠብቁም!
=========================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ክርስትናን ያልጮች መናኃርያ ያደረጉት የሚኖሩትን አልጫነት አጽድቀው የሚያስተምሩ መምህራን ናቸው። እነርሱ የተቀበሉትን ባርነት ሌላውም ተቀብሎ እንዲስተካከላቸው ይፈልጋሉና፤

አንድም ከአልጫነቱ ሌላ በትምህርት የሚያውቁትን ጀግንነት በኑሮ አልተገለጡበትምና ጀግንነት አውሪ ባልጫነት ኗሪ ትውልድ ያሳድጋሉ።

ይህም ቢኾን ግን ተጠያቂነቱ በእነርሱ ላይ ብቻ አይቆምምም፤ እነርሱ ይህንን ሲሠሩ ዝም ያልናቸው፣ በሀገር ቤትም ኾነ በውጭ የምንኖር ይህንንም ማስቆም ያለብን፣ የነበረብን፣ ልናስቆመውም ጸጋው የተሰጠን እኛ ወንዶች ነበርን።

"ድሮም ብዬ ነበር" ብሎ ማላዘን የአቅመቢስ፣ እያላዘነም የሚሸቅለው ሆዳደር ጠባይ ናቸው። ልክ እንዳልነበረ አስረግጠን ስናውቀው ተከታይና ደጋፊ፣ አጨብጫቢና አራጋቢ ከመፈለግ ይልቅ አንድ መድኃኔያለምን ይዘን መጀመሪያ እኛ ተሠርተን፣ ሲቀጥል ሀሳባችንን ገዝተው የሚቆሙና የሚዋደቁትን ጥቂት አፍርተን ብንሞግት፤ ሞተንም ቢኾን ኖሮ ለውጥ እናመጣ ነበር።

ነገር ግን እነዚያ ኾን ብለው ትውልዱን አልጫነት ሲግቱት እኛ ደግሞ ትክክል አለመሥራታቸውን እያየን ስደትና ግዞትን ፈርተን ለትውልዱ ያልጫ ምሳሌ ኾነነዋል!

እነዚያ አስቀድመው ራሳቸውንም ኾነ የወከሉትን ተቋም አይነኬ፣ አይሳሳቴ፣ አይሞገቴ አድርገው ሲሾሙ በውስጠ-ታዋቂነት ራሳቸውንም እንዲሁ አድርገው በማቅረብ ነው።

ከዚህም የተነሳ ዛሬ ዛሬ አንድ መስተካከል የሚፈልግ ያለበትም ጉዳይ ይዛችሁ እነርሱ ጋር ስትሄዱ "ምን ለማለት ፈልገህ ነው፦ ቤተክርስትያን ትሳሳታለች፣ ሲኖዶስ ይሳሳታል፣ አባታችንን ተሳስተዋል እያልክ ነው፣ ለቤተክርስትያንስ ያለላት አንድ ማኅበር ይሳሳታል....?" ይሏችኋል።

ተብያለሁና እንዲህ አልኩኝ!

ወንድምዓለም! ምንደኞች በትምህርት አሰስነቱን አጽድቀው፣ አልጫነቱን መንፈሳዊነት ብለው ለጋቱት ትውልድ፤ አንተ አስረግጠህ በምታምነው እውነት የሚደርስብህን ስደትና ግዞት ፈርተህ ለአልጫነቱ አርኣያ አትኹነው!

እነዚያ ስሕተት በማስተማር ሲያልጩት፤ አንተ ግን እውነትን በመሸሽ፣ እርሷ የምታስከፍለውንም ዋጋ በመፍራት አልጫነቱን በተግባር ታጸናበታለህና!

👉 ባፍጢም ከተደፉ፣ ለልጆቻቸው ከማይራሩ፣ ዳቦ ጠይቀዋቸው ድንጋይ ከሚሰጡ ሆዳደር ምንደኞች በቃል፤

👉 እውነትን ሲያውቋት ሐሰትን ሲለይዋት ነገር ግን ብንመሰክር እንሰደዳለን ብለው ካገኙ በልተው ካጡ ተደፍተው ለማደር በቆረጡ ስዱዳን አልጮች በተግባር፤

🌟 ትውልዱን የወጣለትና የተዋጣለት አልጫ አድርገን አሳድገነው ካበቃን በኋላ ራሱንም ኾነ ማኅበረሰቡን ቤተክርስተያኑንም መታደግ ሲያቅተው ማላዘን፦ ያልዘሩትን ለማጨድ መናፈቅ ነው።

ስለኾነም ትውልዱን አባቶቹ ወደኖሩበት፣ አባቱ በልጅነት ሥልጣን እንዲኖር፣ እንዲገዛ፣ እንዲነግሥ ወደ ጠራው ልዕልና ከወደቀበት ያልጫ ስብዕና ማንሳት ያስፈልጋል።

አለበለዚያ ግን በቃልና በተግባር ከቀደሙት ያየውና የቀሰመው የጸደቀ አሰስነት፤ እንዲኹም ደግሞ "መንፈሳዊነት ነው" ተብሎ የተነገረውና የሚያውቀውም፦ አልጫነት ኾኖ ሳለ ትዳርክን፣ ቤተሰብክን፣ ቤተክርስተያንንና ሀገርክን ትታደግ ዘንድ ተነስ ማለት በእርሱ መዘበት ነው።

አሁንም ትውልዱን "አልጫነትን መንፈሳዊነት ነው" እያላችሁ አሰሰነቱንም ጽድቅ እያደረጋችሁ የምትግቱት እናንተ፤ እንዲሁም እውነቱን ስታውቁት ሐሰቱን ስትለዩት እንዲያ መመስከር ፈርታችሁ ተደብቃችሁ የምታንሾካሽኩት እናንተ ለጥፋት ጉስቁልናው ለሙስናውም ተጠያቂ ናችሁ!

በቃልም በተግባርም አልጫ አድርጋችሁ ካሳደጋችሁት፣ እዳይረባም እንዳይለማም አድርጋችሁ ካኮላሻችሁት ትውልድ ትድግናን ይፈጽማታል ብላችሁ አትጠብቁ!

አልጨረስኩም ይቆየን እንጂ!

አባወራ

28 Nov, 03:15


ጎጂ ወንድነት አለን?
=============
https://youtu.be/ePkgZg9sPBo?si=WlVmTBy4tYiq5_0q

አባወራ

27 Nov, 09:16


ተልዕኮዎች በፎቶ ሲዘከሩ
================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

እስቲ በእነዚህ ፎቶዎች መካከል ያለውን ግንኙነት፣ ተዛማጅነት፣ ተያያዥነት፣ ተከታታይነት እና በመካከላቸው ሊኖረው የሚችለውንም መርሓዊ ግንኙነት አጢኑ!

አባወራ

26 Nov, 13:56


ወንዶቻችንን አልጫ ሽልጥልጥም የማድረግ ዘመቻ
=================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

በቤተክርስትያናችን ማለትም በኢኦተቤ በዚህ በያዝነው 2017 ዓመት በርብርብ የሚሠራ ሥራ ነው፦ ወንዶች ከተሰጣቸው ጸጋ ገፎ፣ መክሊታቸውን ቀብሮ፣ ወደ አልጫነት ብሎም ሽልጥልጥ የማድረጉ ዘመቻ።

ሥራው በዋናነት በሁለቱ ተቋማት፤ በተዋረድት ደግሞ እነርሱን በተከተሉ በርካታ ንዑሳን ተቋማት ይሠራል። የመጀመሪያውና ቀዳሚው ክንፍ መሰል ፕሮጀክቶችን በቤተክርስተያኗ ስም በሚዋዋለውና የትግበራ ኃላፊነቱን በሚረከበው የኢኦተቤ ልማትና ክርስትያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ሲኾን ሁለተኛው ክንፍ ደግሞ በማኅበረቅዱሳን በኩል የሚሠራ ነው።

በሁለቱ ክንፎች ስር በመኾን በንዑስ አካልነት ደግሞ በቤተክርስተያኗ ውስጥ የተለያየ ዐላማን ይዘው በግልጥ ነገር ግን አልጫና ሽልጥልጥ ወንዶችን አመጸኛና ግትር ሴቶችን በስውር የሚያፈሩት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ብቅ ብቅ ያሉት የወጣቶች፣ የኪነጥበብና መሰል ማኅበራት ናቸው።

ለሁሉም እንደ ዓላማ ዓላማ ከወንዱ ወንድነትን መግፈፍ ተልዕኮም ሲይዙ ይህንንም የተለያዩ በሚመስሉ ተመሳሳይ መርሐ-ግብሮች በሥርዓተ ጾታ፣ በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ምሥረታ፣ በጾታዊ ጥቃት፣ በሴቶች እኩልነት፣ የሴቶች አመራር እያሳበቡ በችኮላና በከፍተኛ ጥድፊያ እየፈጸሙት ይገኛሉ።

የሥራቸው ጥድፊያ ሸፍጣቸውን ለተረዳ እንጂ ለአብዛኛው የዋህ ምዕመን ይህ ዐይታየውም። ኾኖም ግን እሳት ላይ የተጣደው ውሃ ቀስ በቀስ መፍላቱን እያለማመዳት ቀቅሎ እንደገደላት እንቁራሪት ውድቀታችንም እንዲሁ ቀስ በቀስ ሞታችን ግን ድንገት አንድ ጊዜ እንዲኾን አስተውሉ።

ቀስ በቀስ ትውልዱን ከትውልዱም ወንዱን በተለይም በማኅበራት እያቀፉ ማለጭ ማሽለጥለጥም ከቤተክርስተያኗ ይኹንታ ያገኘ ይመስላል።

ወንድምዓለም! ወንዶቻችንን እያጣናቸው ነው! ሆዳደርነት፣ አልጫነት፣ ሽልጥልጥነትም የቤተክርስተያኗ ወንዶች በተለይ ዘመናዊ ትምህርት ቀሰሙ ከሚባሉቱ እየተዘወተረ ነው።

የትውልድ አርኣያ ይኾናሉ ብለን የጠበቅናቸው ወንዶች አልጫ ሆዳደር ሽልጥልጥም እየኾኑ በርካታ ተተኪዎችን ሳያፈሩ መፍጠን ይገባናል።

እንኳን ለቤተሰብ፣ ለማኅበረሰብ፣ ለቤተክርስተያንና ለሀገር የሚተርፍ ወንድ ይቅርና ለአንድ ሚስቱ የሚኾን ኹነኛ አባወራ እንኳ (አባወራነቱ እየተኮነነ አልጫነቱ እየጸደቀ) እያጣን ነው።

transforming masulinity በAct Alliance ግምገማ ገና ከጅምሩ በኢትዮጵያ ውጤታማ ነው ተብሏል። እንግዲህ የተዶለተልን ምን ያክል እንደሠራ ነገ የምናየው ይኾናል።

ይህ ፕሮጀክት ቀደም ብሎ በዚሁ ተቋም በዴሞክራቲክ ኮንጎ፣ በዝምቧቤ፣ ሩዋንዳ፣ ኡጋንዳ የተተገበረ ሲኾን በውጤቱም በተለይ በዴሞክራቲክ ኮንጎና ዝምቧቤ ሴቶችን በእኩልነት፣ በተሳታፊነትና በአመራርነት ወደ ዲያቆንነት አገልግሎት አምጥቷል።

ነገስ? እኛ ጋርስ?

ዛሬውኑ እነዚህ መጻሕፍትና ሥልጠናዎች እንዲቆሙ ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ ድምጾትን ያሰሙ!

https://chng.it/BGPB2rr4yT

አባወራ

26 Nov, 03:04


ዐዲሱ ወንድነት ሽልጥልጥነት
==================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ሽልጥልጥነት፦ ቃሉ ልክ እንደ አልጫ ሁሉ ኢ-መደበኛና ለወንድ የኾነ ጠባይ የሚገለጽበት የንግግርም ቃል እንጂ መጽሐፋዊ አይደለም። ይኹን እንጂ አሁን ባለንበት ጊዜና ዘመን እያወጣን ያለነውን በወንድነት ጠባይና ግብር የማይገኘውን ትውልድ ሲገልጠው፤ ለመግባቢያነትም የበለጠ ተመራጭ ያደርገዋል።

ትርጉሙ፦ አቋም፣ ቁርጥ ሕሊና፣ ድፍረት፣ ጥንካሬ የመሳሰሉትን የወንድ ባሕርያቱን ከነ አለባበሱና አኳኋኑ የረሳ፤ በሰማውና ባመነበት ጉዳይ የማይጸና፣ የማይቆምለትም ልምጥምጥ፣ ሙልጭልጭ፣ ልፍስፍስ የኾነውን ወንድ እንገልጽበታለን።

በሂደት ከተሸረሸረው ወንድነቱ የተነሳም የወሲብ ፍላጎቱና የተራክቦ ምርጫው በውል ያለየ፣ ያለየለት፣ ግራም የተገባ የሚያጋባም እና የመሳሰሉትን እንገልጥበታለን።

ሰውነት ተፈጥሮአችንን፣ ወንድነት መክሊታችንን አውቀን፣ ሠልጥነንበትና በልጽገንበትም መኖር ግድ የሚለን ጊዜና ዘመን ላይ መኾናችንን ልታውቁት ይገባል።

"ጤናማ ነው፣ ተገቢ ነው፣ ልከኛ ነው" የምትሉትና የሚመስላችሁም የሕይወት መንገድ(lifestyle) እናንተንም ኾነ ትውልድን ከተፈጥሮአዊ ሚዛኑ፣ ከተፈጥሮአዊ ልኩ፣ አያቶቾቻን ከኖሩበት ወጉ ፈቀቅ እያደረገ ይገኛል።

በተለይ ወላጆች የኾናችሁ፣ የነገዋ ኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ የቤተክርስትያንም ሕልውና ግድ የሚላችሁ አስተውሉ! ይህ ለራሳችሁና ለትውልድ ደንታ ስትሉ ትኩረት እንድትሰጡት፤ ከሌሎች ውድቀት በቅርብ ከታዘብኩት እንድንማርበት ፈልጌ የምነግራችሁ ነው።

ልጆቻችን በተለይም ወንዶቹ ከመቼውም የሰው ልጅ ከኖረባቸው ዘመናትና አዝማናት ይልቅ ከፍተኛ የወንድነት ቀውስ ተጋርጦባቸዋል።

ዛሬ ዛሬ በሄዱበት መንገድ፣ በተሰማሩበት መስክ ከወንድነት መክሊታቸው በልጽጎ የሚወጣ እውነትን ይዞ፣ ጽድቅን ዐልሞ፣ ፍትሕን እንዲፈጽም የተሰጠ ባሕርያቸው ይናቃል፣ ይወገዛል፣ ይኮነናልም።

ከዚያም ይልቅ አሰስነትን ጽድቅ፣ አልጫነትን መንፈሳዊነት፣ ሆዳደርነትንም ዘመናዊነት እያሉ ይግቷቸዋልና የሚሰሙትንና የሚውሉበትን ተጠንቀቁላቸው።

አለበለዚያ ግን በየዕለቱ የሚያዩትና የሚሰሙት ከዚያም የተነሳ በኑሮ የሚመላለሱበት ልምምድ በጊዜ ሂደት ተፈጥሮአዊ ወንድነታቸውን አሳጥቶ በሽልጥልጦቹ መንገድ ላይ ይጥላቸዋል።

ያ የወደቁበትን የጥፋት መንገድ መገሰጽ፣ ማስተካከልና ማረም የሚገባቸው አካላት ጭምር ዛሬ ባፍጢማቸው ተደፍተው፣ በሆዳቸው ተገዝተው፣ ዝናና ገንዘብ ሲያሳድዱ ወንዶቻችንን ግን እያጣናቸው መጥተናል።

ወንድ አጥተናል! ወንዶቻችን ሽልጥልጥ ኾነውብናል!

ሀገር፣ ቤተክርስትያን፣ ቤተሰብ በተለይም ደግሞ ሴቶች ያን መከታ፣ አለኝታ፣ ጠበቃ ኾኖ የሚመራቸውን ወንድ ሽልጥልጥ ኾኖ አጥተውታልና እጅጉን ተበድለዋል!

ታናሼ አስተውል! የኖርንበት፣ ትውልድና ሀገር የተገነባበት እውነት ሁሉ ኾን ብለው ግራ ያጋቡ ዘንድ በተላኩ ቅጥረኞች በሚያወዛግብም ርዕዮት ይፈርሳል።

በዚያ በሽልጥልጦች መንገድ፦
👉 ጾታን ሁለት ዓይነት ነው፣
👉 ለጾታዊ ሚናም መገኛው ጾታው ነው፣
👉 ጋብቻ በወንድና በሴት መካከል ነው፣
👉 ቤተሰብ አስፈላጊ መሠረት ነው፣
👉 ቤተሰብ በባልና በሚስት(በወንድና ሴት ጋብቻ) ይመሠረታል፣
👉 ወሲብም ከተቃራኒ ጾታ ጋር ብቻ ይደረጋል፣ የሚሉት፦ ወንዶች በተለይም በአባታዊ(በአባወራዊ) ሥርዓት ትውልዱን የሚመሩት ናቸው ተብሎ ይኮነናል።

አሁን ለጊዜው ይህንን ከአባታችን በአባቶቻችን በኩል የተቀበልነውን ሥርዓት ፊት ለፊት አያወግዙትም። ነገር ግን ከሚግቱን ሸፍጠኛ "ሥልጠና" የተነሳ እኛው ራሳችን ነገ በአባታችን ላይ አምጸን እንኮንነዋል እንጂ።

ስለኾነም ከመሠረቱ በዚሁ ግራገብ ትርክት ግራ ተጋብቶ የሚያድገው ትውልድ እርሱኑ የሚያርምለት፣ በተለይም በተግባር ቀና የኾነውን ተፈጥሮውን ኖሮ ተገልጦበት የሚያሳየው አባት ሲያጣ ሰለባቸው ይኾናል፤ ይሰለባልም።

ወንድምዓለም! ድሮ ድሮ ወንዶች ይገለጹባቸው፣ ይታወቁባቸው የነበሩ ባሕርያት ጠባያትም ዛሬ፦ ያረጀው፣ ያፈጀው፣ ሊቀር የሚገባው የአንባገነኑ አባታዊ ቅጥ፣ አባወራዊ ሥርዓት ናቸው ተብለው ይኮነናሉ።

ይህ ዐይነቱ ፍረጃ በቤተክርስትያን ትምህርቶች፦

🌟 ባፍም ኾነ በመጣፍ መዘውተራቸው፣
🌟 የመርሐ-ግብሮቹም ይዘትና አቀራረባቸው፣
🌟 የመድረክ ዝግጅቱና አካሄድም የወንዶቻችንን ሽልጥልጥነት የሚያበረታቱ፣ የሚያስፋፉና የሚያጸኑ እየኾኑ መምጣታቸውን አስተውሉ!

ልጆቻችሁን በተለይም ወንዶቹን ከዚህ መሰሉ በተሰጣቸው የወንድነት ጸጋ ከመበልጸግ የሚያግዳቸው፣ በጾታ ግራ ገብነት የሚያጠፋቸው፣ ወደ ሽልጥልጥነትም የሚያመራቸውን ማንኛውም እንቅስቃሴ በንቃት ተከታተሉ።

ዛሬ የመዝሙሮቻችን፣ የዘፈኖቻችን፣ የፊልሞቻችን፣ የማስታወቂያዎቻችን፦ መልዕክት፣ አቀራረብ፣ የተዋናዮቹ አኳኋንና አለባበስ ሁሉ ይህንኑ ሽልጥልጥነት የሚያበረታታ ኾኖ አግኝቼዋለሁ።

ሰሞኑን ሳካፍላችሁ ከቆየሁት በቤተክርስትያናችን (በኢኦተቤ) እና በባለድርሻ አካላቱ transforming masculinity ወንድነትን ማሻገር በሚሉት ሸፍጠኛ ፕሮጀክታቸው ኦርቶዶክሳዊ የኾነውን ወጣት በተለይም በሰሜኑ ክፍል ላለው ወንድ ሽልጥልጥነትን ማሠልጠን ታስቧል።

ምንም እንኳ የቤተክርስተያኗ ማኅበራትና ሰንበት ትምህርት ቤቶች የዐዲስ አበባን ኦርቶዶክሳዊ ወጣት፤ ከወንድነት ቁመናው ከአባወራነት ልኩ አወርዶ አልጫ በማድረጉ ሂደት ከፍተኛ ሚና ቢጫወቱም እንኳ ለእነርሱም ሥልጠናው አይቀርላቸውም።

አንተ የተኛህ ንቃ!

ጠላት የተከተልካቸውን እረኞች፣ ያመንካቸውን መሪዎች ተጠቅሞ አባትህና አምላክህ የሰጠህን ወንድነት መክሊትህን ቀብረህ፣ ከጸጋው ርቀህ በኃጢያት ቀንበር ሊያኖሩህ ታጥቀዋልና አስተውል!

እንዲህ ዓይነቱን ትውልድን ለጾታዊ ግራገብነት ዳርገው ከሚያራግቡት ምዕራባውያን የስም ኦርቶዶክሶች መካከል አንዷ እንዲህ ትላለች፦

"እግዚአብሄር ቀንና ጨለማን ፈጠረ ማለት በመካከሉ ወጋገን፣ ንጋት፣ አመሻሽ፣ ምሽት የሚባሉትን አልፈጠረም አይባልም።

ለጾታም እንዲሁ ነው። ወንድና ሴት ፈጠረ ማለት በመሃል ያሉትን አልፈጠረም አይባልምና በጾታዊ ግራገብነት ያሉትን እነርሱን ልትቀበሏቸው፣ ልታበረታቷቸው፣ ልታሳትፏቸውም ይገባል።"

ይህ እንግዲህ የሁለት ዓይነት ጾታ እውነትን በተቀበለ ማኅበረሰብ ውስጥ፣ በዚያው ቅጥ ራሱንና ልጆቹን የሚመራ አባወራና ሥርዓቱን ግትርና አንባገነን ነው እያሉ በመፈረጅ ትውልዱንም በማሳመጽ ለርኩሰትና ሞት የሚያለማምዱበት መንገድ ነው።

በዚህም ሥልጠና መሠረት ትውልድ ዐዲሱን ወንድነት እርሱም ሽልጥልጥነትን እንዲቀበል፣ እንዲኖረውና ያንኑም የመንፈሳዊነቱ ጥግ አድርጎ እንዲቀበለው ይደረጋል።

"ልጆቻችን ከክፉ ቦታ ርቀው ቤተክርስትያን ይውላሉ" ስትሉ ቤተክርስትያን ሄደው ምን፣ ስለምንና እንዴት እንደተማሩ ጠይቁ። "ምድርን በመዝሙር አንቀጥቅጠናት መጣን" ዐይነቱንም ፈሊጥ በዐይነ ቁራኛ ልታዩት ልትመረምሩትም ይገባል።

በእነዚህ ጾታዊ ጥቃት እያሳበቡ አባትነትን፣ የአባታዊ ሥርዓትን፣ የአባት የኾነውንም ሁሉ በመቃወም፣ በእርሱ ላይ በማመጽ ሥርዓቱን በማጥፋትም ዐዲስ ወንድነት እርሱም ሽልጥልጥነት ይገኛል።

የምለው ግን ይገባችኋል ወይንስ...?

አባወራ

25 Nov, 05:31


በአልጮች ትውልዱን ማለጭ
https://youtu.be/sXVPv34nhYE?si=LRRFNlXDkTcHwkEe

አባወራ

21 Nov, 03:41


ግዴለሽ እረኛ ከተኩላ ይከፋል
===================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

በጎቹ ለሚሰማሩበት ለሚውሉበት ቦታና ለሚበግጡትም ግድ የለሽ የኾነ እረኛ ከመንጋው መካከል ሊለያቸው ሊነጥቃቸውም ከሚመጣው ተኩላ ይከፋል።

ምክንያቱም በጎቹ እርሱን አምነው የሚወጡ፣ እርሱን ተከትለው የሚሰማሩ፣ ድምጹን ሰምተው የሚከተሉት ናቸውና ከወሰዳቸው ቦታ ይውላሉ።

ነገር ግን እርሱን አምነው የወጡበት ቦታ የተኩላ ሰፈር ከኾነ፤ አንድም እርሱን አምነው የሚግጡት ሳር ለተፈጥሮኣቸው የማይስማማ ሆዳቸውን ነፍቶ፣ ደረታቸውን ሰፍቶ፣ ባፍጢማቸው ደፍቶ የሚፈነግላቸው ከኾነ እርሱ ግዴለሽ ከተኩላውም የባሰ አረመኔ ነው።

ምክንያቱም በጎቹ የሚሰማሩበትን ቦታ እርሱ የመረጠላቸው እንጂ እነርሱ ጠይቀው፣ ለምነው፣ ተለማምጠው ቸወጡበት መስክ አይደለምና በአዋቂው ሰውነቱ ሊወስዳቸው የሚገባውን ቦታ መምረጥ የእርሱ ኃላፊነት ነበርና።

አንድም ደግሞ የሞትን አደጋን ጥፍሩ ከሾለው፣ ጥርሱ ከገጠጠው፣ ዐይኑ የፈጠጠው ተኩላ ይጠብቃሉ እንጂ እረኛቸው የእነርሱን ደኅንነት ችላ ብሎ በግዴለሽነት ካሰማራበት ቦታ ሞታቸውን እንዲህ ይኾናል ብለው አይጠብቁም።

አንድም ደግሞ በጎቹ ያ ዐይኑን ያፈጠጠ፣ጥርሱ ያገጠጠ ተኩላ ቢመጣባቸው ጮኸውም ሮጠውም ለማምለጥ ይሞክራሉ፤ ከዚህ እረኛቸውን አምነው ከተሰማሩበት የሞት መስክ ምኑን አውቀው፤ ተያይዘው ሁሉም ፍግም እንጂ!

C.S.Lewis: Of all tyrannies,a tyranny sincerely exercised for the good of its victims may be the most oppressive. 

ከጨቋኝ፣ አንባገነን፣ በዝባዥ ሥርዓቶች ሁሉ ሕዝብን ለመጥቀም ተብሎ የሚሠራው ሸፍጥ እርሱ ከጭቆናዎች ከግፎችም ሁሉ ይከፋል

ለማንኛውም ያዘጋጀነውን እየፈረማችሁ👇
https://chng.it/BGPB2rr4yT

አባወራ

20 Nov, 05:12


https://youtu.be/iEX02D1dZH0?si=Nq3EkpdgGDsnNCQH

አባወራ

19 Nov, 17:27


ኢትዮጵያዊ፣ ኦርቶዶክሳዊ፣ አባወራዊ ኃላፊነትና ግዴታ

https://chng.it/BGPB2rr4yT

አባወራ

19 Nov, 09:28


እኛ ልጆቿ ላይ ጥፋት ያወጀችው ቤተክርስትያን
=================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ዶሮን ሲያታልሏት በመጫኛ ጣሏት ይላል ያገሬ ሰው። ከአምስት ቀናት በፊት በታወጀው የማኅበረ ቅዱሳን ዜና ላይ አርዕስተ ዜናው "ቅድስት ቤተክርስተያን በደን ልማት ፕሮጀክት የላቀ አተገባበር በማሳየት በዓለም አቀፍ ደረጃ ቀዳሚ በመኾን እውቅና እንደተሰጣት ተገለጸ" ይላል።

ዝርዝሩ ውስጥ ደግሞ ቅድስት ቤተክርስትያን እውቅና የተሰጣት የልማትና ክርስትያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን ባከናወናቸው ተግባራት ሲኾን፤ ኮሚሽኑ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ማኅበረሰቦችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን እያከናወነ መኾኑ ተመላክቷል ይላል።

ከዚያ በመቀጠልም የልማት ኮሚሽኑ ኮሚሽነሩ በመቅረብ ቤተክርስትያኗ የተመረጠችበት በደን ልማት ቀዳሚነት ማገናኘቷን ያስረዳሉ።

ይኹን እንጂ ይህንን እርስበእርሱ ያልተገናዘበ የዜና ሽፋን ገለጥ አድርጌ የልማትና ክርስትያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን Act Alliance ከሚያስቀድማቸውና ከሚያራምዳቸው ዓላማዎች አንጻር ተመራጭ ሊያደርገው የሚችለውን ሥራ ስመረምር ከአሁን በፊትም ኾነ በተለይ በ2017ዓ.ም. በዘመቻ ሊሠራ የታቀደው "የሥርዓተ-ጾታ" ሥልጠና ላሰጡት ፈቃደኝነት የተሰጠ እውቅና ኾኖ አግኝቸዋለሁ።

የኢኦተቤ በደን ልማት ዙሪያ ከቀድሞ ዓመታትና ዘመናት የተለየ የሠራችው የተለየ እንቅስቃሴ ኖሮ፣ ቢኖርም ይህን ያክል ዐለም አቀፍ እውቅና የሚያስገኝም አይባልም።

ይልቁንስ ከዚህ በፊት ባጋራኋችሁ ኮሚሽኑ ተቀብሎ እንዲያሳትም፣ አሳትሞም እንዲተገብራቸው ባስመረቃቸው ሁለቱ መሠልጠኛ መጻሕፍት አማካኝነት ዐዲስ አበባን ጨምሮ በአማራ ክልል ውስጥ ባሉ 26 ወረዳዎችና 76 ቀበሌዎች የሥልጠና ዘመቻውን እንዲያፋጥን እንጂ።

(መጻሕፍቱ የሚሠራጩት የሥርዓተ ጾታ ሥልጠናውም የሚሰጠው በዐዲስ አበባና በአማራ ክልል ብቻ መኾኑ ቤተክርስተያኗ ከሌሎች ልጆቿ ለይታ የምትሰጥበትን ምክንያት ያስመረምራል!

ሰሞኑን እንኳን ሥልጠናው ሊሰጥ ቀርቶ ለእርሱ የተዘጋጁት የሥልጠና መመሪያዎች ራሳቸው መሠራጨት የለባቸውም ያልኳቸው መጻሕፍት በAct Alliance ትብብርና ድጋፍ የታተሙ ናቸው።

Act Alliance ደግሞ እንደ Tearfund , Angelican Communion, Angelican Alliance ተቋማትና እንደ ድልድል ፕሮጀክት ሁሉ Gender Justice ዋነኛና ተቀዳሚ ተግባራቸው ነወ።

Gender Justiceን Oxfam እንዲህ በማያሻማ መልኩ ያስቀምጠዋል፦ justice as the full equality and equity between men, women, LGBTQIA+ and non-binary people in all sphers of life ...

የAct Alliance ድረገጽ ውስጥ ብትገቡም መሰል ትርጉሞችን ስታገኙ፤ በተለይ ደግሞ Gender Justice በሚለው ርዕስ ስር የተቀመጠውን አቋማቸውን ስታነቡ ምን ለመሥራት እንደተነሱ በግልጽ ትረዳላችሁ።

Gender Justice: Challenging patriarchal or other structures of power and creating an enabling environment for gender justice....

አባታዊ (አርበኛዊ) ወይንም ሌሎች የኃይል ተቋማትን መግጠም፣ መቋቋም፣ መፈታተ፣ ማስቆም.... የሚል ትርጉምን የያዘ ነው።

ከላይ መግቢያዬ ላይ ለኢኦተቤ እውቅና ተሰጠበት በተባለው ስብሰባ ውጤት በኾነው ተቋማዊ መግለጫቸው በገጽ ሦስት እንዲህ ይላል፦

👉 Transform harmful gender norms.... which uphold patriarichal structure...., impose determinant standards on girls, women, and gender non-confirming people...

👉 Promote the full realisation of.... LGBTQI+ people.

👉 recognise and implement ... principles... to ensure the human rights of LGBTQI+ people and ... increase funding to LGBTQI+ organization.

👉Engage in... dialogues on the dignity of LGBTQI+ people...

ይህንና ሌሎች መግለጫቸውን ከታች በመልዕክት መስጫ ሳጥን ውስጥ አስቀምጥላችኋለሁ።

ከእነዚህ እና ለሥልጠና ከተዘጋጁት እንዲሁም ከAct Alliance አቋም አንጻር ትልቁ ጥላቻቸው አባታዊ ሥርዓት እንደኾነና ሥራቸው ሁሉ እርሱን ለማስጠላት፣ ለማስናቅ፣ ለማሳመጽና አባታዊ መዋቅሩንም ለማፍረስ እንደኾነ ትረዳላችሁ።

ይህ ደግሞ የቀደመው እባብ በአዳምና ሄዋን አባት ላይ እነርሱ ከሕጉ እንዲወጡ ከሥርዓቱ በማሳመጽ የሠራውን ሸፍጥ ይመስላል።

ወደድንም ጠላንም ክርስትና ሐይማኖታችን አባታችንን የምናመልክበት አባታዊ ምሥረታ ዓት ነው። ከላይ የተቀመጠው ሁሉን የፈጠረው አምላክ አባታችን ሲኾን የዘረጋውም የእርሱ መዋቅር አባታዊ ነው።

የአባቶቻችን የአብርሃም፣ የይስሃቅ፣ የያዕቆብም አምላክ እንድንል ስለኾነም ከዚህ በተቃራኒ የምትንቀሳቀሰው ቤተክርስትያን ልጆቿ ላይ ልታመጣ ያለችውን መቅሰፍት ብትመረምረው ይበጃል!

አሁንም እነዚያ በፈጣሪ አባታችንም ኾነ በወላጅ አባቶቻችን ላይ አመጽን የሚያስተምሩ፣ ከሥነ-ሥርባር ያፈነገጡ በትውልዱ በተለይም በወንድና በሴቲቱ፣ በባልና በሚስቲቱ በአባትና በእናቲቱ መካከል፦
🌟 ልዩነትን፣
🌟 ጥርጣሬን፣
🌟 ስጋትን፣
🌟 አለመተማመንን፣
🌟 ጥላቻን፣
🌟 የጸብ... የሚያመጡ መጻሕፍት እንዳይበተኑ ሥልጠናዎችም እንዳይሰጡ ልናደር ይገባል!

በተጨማሪም ከነባር ሥርዓቱ በተለየ ሁሉን አካታች፣ አሳታፊ፣ አስተካካይ በሚሉ ፈሊጦች ኃጢአትንና እርኩሰትን፣ ጉስቁልናና ሞትን በማኅበረሰቡ ውስጥ ማስገባትና ማለማመድም ዓላማቸው ነው!

ከላይ በዘረዘርኳቸው ሸፍጠኛ አማካኝነት ውጤታማ ኾነውበት ቤተክርስትያኗንም ኾነ ትውልዷን ካፈረሱባት ሀገር አንዷ እንግሊዝ ናት።

ቤተክርስትያን ልጆቼን አለማበታለሁ ብላ በዘረጋችው ክንፍ እርሱም የልማትና ክርስተያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን አማካኝነት ሞትና ሙስናን በእኛ በልጆቿ ላይ ማወጇን ምን ያክሎቻችሁ ታውቃላችሁ!

አባወራ

19 Nov, 04:06


መክሊት ወንድነትክን ኮነነ በባርነት ሊረግጥክ ደነደነ
===================================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

(ደነደነ= የጦር ሠራዊት አደራጀ፣ አዳበረ፣ አደነደነ፣ አከማቸ፣ ሰብሰበ፤ በጉልበት በጦርነቱ ትምህርት አደነደነ፣ አሠለጠነ፤ ከሣቴ ብርሃን ተሰማ አማርኛ መዝገበ ቃላት)

የሰውን ልጅ በባርነት ልትገዛ የምትፈልገው ዐለም የባርነት ቀንበሯን ለመጫን ያቀልላት፣ ያፈጥንላትና ያረጋግጥላት ዘንድ ትውልዱ ባርነትን የሚመክትበት መክሊቱን እንዲኮንን ታስተምራለች።

በተለይም ወንዱ ተፈጥሮውን አውቆ፣ አበልጽጎና ሠልጥኖበትም እንዳያይል(ኃይለኛ እንዳይኾን) ወንድነቱ ለመንፈሳዊ እድገቱ እንቅፋት እንደኾነ፣ አሰስነት አልጫነቱን አጽድቃ ትግታለች።

ስለኾነም ፈተናን የሚጋፈጥበትን፣ መከራን የሚገጥምበትንና ድለኛ ኾኖ ራሱን ቤተሰቡን፣ ተቋማቱን፣ ትውፊቱንና ሀገሩን የሚታደግበትን ወንድነቱን ታስጥለዋለች።

አንድም ወንዱ በፈተና የሚሠራ፣ በመከራም የሚጸናና የሚታነጽ ወንድነቱን፤ ፈተናን እንዲሸሽ፣ መከራን እንዲፈራ ሲደርስበትም እንዲያዝንና እንዲያላዝንም በመምከር ከወኔው ትሰልበዋለች።

ትውልዱ አባቱ የሰጠውን ወንድነት ከጠላና ከጣለው፦ በእውነት መንገድ ቀድሞ የሚመራው፣ ፍትሐዊ በኾነ ዳኝነት የሚያሳርፈው፣ በጽድቅም ቤዛ ኾኖ የሚያገለግለው መሪ-ራስ እንዳይወጣው ጠላት ያውቃል።

አንድም ደግሞ እንዲህ የተሰለበው ወንድ በበዛበት ማኅበረሰብ ትውልድ ለብዝበዛና ለምዝበራ ለጉስቁልናም ወዶ የተሰጠ ምርኮኛ እንዲኾን ሆዳደር ምንደኞች በጠንቅቀው ያውቃሉ።

ስለኾነም አስቀድሞ ወንድነት ተፈጥሮውን በጥቅሉ፣ ድፍረት፣ ጥንካሬና ሥልጣኔውን በዝርዝሩ እየለዩና እየቆጠሩ ይኮንናቸዋል፤ በእርሱ ፈንታም አሰስነትን አጽድቀው ወደ አልጫነት ሞሽረው ወደ ባርነት አውርደውና አዋርደው አሳልፈው ይሰጧቸዋል።

ታናሼ! ወንድነት መክሊትህን ከተፈጥሮህ፦ ለይተው፣ ከሰውነትህ አርቀው፣ ሲኮንኑ፤ ባርነት የሚያመጣ አልጫነትክን እያጸደቁ ሲግቱህ ያን ጊዜ ተጠንቀቅ!

እነርሱ በባርነት እየደፉና እያዳፉ ሊወስዱህ የፈለጉ ጠላቶች አልያም እንደዚያ ለሚነዳህ አሳልፈው የሚሰጡህ በዘመናዊነትና በመንፈሳዊነት ስም የሚሸጡህ ሆዳደር ምንደኞች ናቸውና!

ወንድምዓለም! በፈተና የሚታነጽ፣ በመከራ የሚሠራ፣ በችግሮችም መካከል የሚሳል ወንድነት ተፈጥሮህ አባትህ አንተን መሪ-ራስ ላደረገበት ኃላፊነት ኹነኛ መሣሪያህ ነው።

ምንደኞች እርሱን የሚኮንኑት በተለይም በመንፈሳዊነት ስም አሰስነት ተቃራኒውን አጽድቀው የሚግቱት የማይጠይቅ፣ የማይሞግት፣ ራሱንም ኾነ ቤተሰቡን የማይታደግ ፍዝ፣ ድንዝዝ፣ በመዝናናትና በመዳራትም የተሰለበ ወንድ ስለሚፈልጉ እንጂ።

ስለኾነም ስለተሰጠህ ሰውነት ተፈጥሮህ ወንድነትክም ቢሉ መርምር እወቅ፤ ባወቅከው ልክ ደግሞ ኑር። ብዙ አውቅሁ ብለህ ብዙ አታውራ፤ ካወቅከው የኖርከውን በተግባር የተገለጥክበትን ለጠየቀህ ያንኑ አስረዳ እንጂ።

አለበለዚያ ግን ስታወራ ብዙ የምታውቅ መስለህ፣ ኖረኸው በፈተና ታሽተህ የወጣህበት ተግባራዊ ልምምድም ከሌለህ፦ አስመሳይና ሸቃላም መኾንህ ሲታወቅ ታናናሾችህን ታስታለህ!

እርሱም በትምህርት የደረሱበትን ወንድነት በተግባር በፈተና ሳይሠሩበት አንተው እንዳሳየሃቸው የሚያወሩት፣ የሚያንበለብሉት የሚጽፉትም ይኾናሉ።

ፈተናን ስትሸሽ፣ መከራን ስትደበቅ፣ ከሰጡህ በልተህ ፊት ከነሱህ እየተነፋረቅክምተደፍተህ እያደርክ፣ ይኸውም ካንተ እንዲርቅ እየለመንክ ወንድነትን "አስተምራለሁ" ማለት አምነው የሚሰሙህን ተከታዮችን ከጠላቶቻቸውና ኮንነው ከሚግቷቸው ምንደኞች የበለጠ ትጎዳቸዋለህ ።

ይኸውም እነዚያን ሸሽተው አንተን አምነው ሲመጡ ወንድነት ባፍ ቢወራ፣ በጽሑፍ ቢከተብ፣ በዩቲዩብና በመጽሐፍም ቢሸቀልበት እንጂ በፈተና የማይገለጥ፣ በመከራ የማይታወቅ ይልቁንስ እነዚህ ሲመጡ የሚሸሸግ፣ እስኪርቁም የሚነፋረቅ አድርገህ ታሳስታቸዋለህና።

ታናሼ! እውነትን ይዘህ በምትኖርበት ዐለም በመከራ ውስጥ ማለፍ ተፈጥሮኣዊ ወንድነትክን የሚገነባ የሚያበለጽገውም ነው። ፈተናና መከራ በመጡ ቁጥር ማዘንና ማላዘን እነርሱን ጠልተህም መሸሽ በወንድነትህ ላይ ጥፋትን ሙስናንም ማምጣት ነው።

ስለኾነም አባትህ የሰጠህ ወንድነት እውነት፣ ጽድቅና ፍትሕ አጥታ የመረረችውን ዐለም የምታጣፍጥበት ጨውነት መክሊትህ ነውና በእውቀት ይበልጡንም ደግሞ በፈተናና በመከራው እሳት በደስታ ታነጽበት!

አባወራ

18 Nov, 14:59


ለቤተሰብዎ ምርጥ ሳሙና! ሜክሲኮ ኖክ ማደያ ፊትለፊት ዘይኑ ኮስሞቲክስ ያገኙታል!
በእጃችን፣ በቤታችን፣ ልጆቻችን የሠራነውን ሳሙና ለምንወዶት ለእርሶም!
ለፊትዎ፣ ለገላዎ ለፀጉሮስ ቢሉ ምርጥ ነው!

አባወራ

18 Nov, 12:02


ለባርነት ማሳለጫ አልጫ፤ ማርከሻ መድኃኒቱ አባወራ
==============================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ባርነት አድፍጣ ከደጅህ ብታደባም ቅሉ፤ ከቤትህ የሚያስገባት ደጁ፣ የምትሾልክበት ሽንቁሩ ግን ከሰውነት የራቀው፣ ከወንድነት የተለየው፣ ከአባወራነት ያልደረሰው አንድ አልጫ ነው።

ትውልዱ ደግሞ አልጫ እንዲኾን ባፍና በመጣፍ፣ በመገናኛ ብዙኃኑና በማትገጹም የጆሮ ታንቡሩ እስኪበሳ በሚደለቅበት ጩኸቱ፣ በሚውረገረግበት ዳንኪራው፣ ዐይኑ ቦዞ በሚፈዝበት ወጉ፣ አስተውሎቱ ፈዞ በሚደነዝዝበት ተረቱ፦ ባርነትን ወዶ፣ ፈቅዶና አደግድጎ መቀበሉ እርግጥ ነው።

እውቀትን የሚገበይበት አንድም እውነት የኾነ እውቀትን ወደ'ሚሸምትበት የጥበብ ገበያ ሳይኾን ሳቅና ስላቅ፣ ተረትና ቀልድ፣ ቧልትና ፌዝ፣ ሽሙጥና ሽርሙጥና በመዝናኛ ስም ለሚጋትበት ገበያ ይጣደፋል፤ ያጣድፉታልምና ይጣደፋል።

ለትውልዳችን እውነት በኾነ ስል እውቀት የመሃይምነት ሞራውን ካይኑ ላይ ሊገፉ ያላቸው ብዙዎች መምህራን፤ ማዕረግና መጠሪያ በሰበሰቡ፣ ከክብራቸው ይልቅ ሆዳቸውን ባስቀደሙ ጥቂት ግለሰቦች ተውጠው ትውልዱ ወደ ባርነት ይቸኩላል።

ወንድምዓለም! ትውልድ ወደ ባርነት የሚነዳበት ኹነኛ መሣሪያው አሰስነቱን አጽድቆ፣ "የድኅነት እውቀት ነው" ብሎ መጋቱ ነው። እርሱም ጽድቅ ይኾንልኛል ብሎ ተፈጥሮውን ከሚያስጥል ስሑት ትምህረት ቢጣባ ለነፃነት መፈጠሩን እንኳ ረስቶ ባርነት-ሞቱን መርጦ ይሞተዋል!

ይሀንን የትውልድን ባርነት የሚያሳልጡት ደግሞ አስቀድመው ያለጩ፣ ብዙኃኑንም ሊያልጩ ከጠላት ተኩላ ጋር በሆዳቸው የተዋዋሉ፣ ባፍጢማቸው ተደፍተው የተማማሉቱ ምንዳ የሚሰፈርላቸውም ናቸው።

አንድም ደግሞ ካልጫነታቸው የተነሳ ካገኙ በልተው ካጡ ተደፍተው ማደርን የመረጡ፤ ሰውነታቸውን በማስትሬትና በዶክትሬት በማዕረግና በመጠሪያ ልክ ሰፍተው ዝምታ በመረጡት ነው!

ጠላት የባርነት ቀንበሩን አሸክሞ ሰተት ብሎ የሚገባባቸው በሮች እነዚሁ አልጫ ሆዳደሮች ናቸው። ለእነርሱ ትልቁ ስኬት፦ ማስትሬትና ዶክትሬት፣ ሊቅነት ሊቃውንትነት፣ ቁሳዊ ሀብትና ታዋቂነት፤ በእነርሱም ልክ የሚሰፈርላቸው ደመወዝና ዝና፣ ከዚያ አለፍ ቢል መዝናኛና መዳሪያው እንጂ!

ታናሼ! ባርነትን በትውልዱ መካከል የሚያሳልጡ የሚያቀላጥፉ፦ ተፈጥሮዋቸውን የካዱ፣ ጸጋ-መክሊታቸውን የቀበሩ አልጮች ናቸው።

ይህንኑ ባርነት የሚያረክሱት መድኃኒቶቹ ደግሞ ተፈጥሮኣቸውን አውቀው፣ በጸጋ-መክሊታቸው በልጽገው በድፍረት፣ ጥንካሬና ሥልጣኔው የሚሰፉኑት አባወራዎች ናቸው።

ሆድን ወዶ፣ ጥቅምን አስቀድሞ፣ ጊዜያዊ ምቾትን መርጦ፣ ለስጋዊ ድሎት አድልቶ፣ በፍርሃት ቆፈንም ተቆልፎ ባፍጢም መደፋት፤ ለንግሥና ለተጠራ የልጅነት ሥልጣንም ለተሰጠው ሰው ውርደት ሞትም ነው!

ዕድሜ እየጨመረ ሲመጣ በእውቀትና በጥበብ ሊያድግ፣ ሊሠለጥንና ሊያሠለጥን የሚገባው ሰው፤ ማርጀት መሸበቱ እንደ እንጨት ከኾነ ለትውልድና ሀገር ኪሳራ ብቻ ሳይኾን ዕዳ ሸክም በደልም ነው።

አልጫነት ከተፈጥሮኣችን ወገን ያልኾነ፣ በተፈጥሮኣችን የሌለ፣ ጥሩ መስሎ እንደ ወረርሽኝ፣ ውሎ ሲያድር በሽታችን፣ ከርሞ ሲጣባንም ነቀርሳ የሚኾንብን ለሰውነታችን ባዕድ ነው።

ለእርሱ መድኃኒቱ፣ ተጋፍጦ የሚጥለው፣ ተጋፍቶ የሚያርቀው አባወራነት ነው! ተፈጥሮን መርምሮ፣ አባታችን የሰጠንን ጸጋ አውቆ፣ የለየልንን መክሊት ተረድቶ በነፍስና በስጋ፣ በደምና ባጥንታቸው ተወራርደው ሀገር እንዳቆዩልን አባቶቻችን በእርሱ አይሎ በመገኘት!

መድኃኒት ደግሞ እንደ ጤፍ ተፈጭቶ፣ እንደ እንጀራ ተጋግሮ፣ በማዕድ በሰፌድ አይቀርብም። ይልቁንስ በመጠን ተለውሶ፣ በብልቃጥ ተቀንሶ በትንሽ በጥቂቱ ይዘጋጃል ይወሰዳልም እንጂ!

ለአባወራም እንዲሁ ነው፦ አልጫ በበዛበት፣ አልጫነት መንፈሳዊነትና ዘመናዊነት ተብሎ በሚገነርበትበት፦ መድኃኒቱ አባወራ በጥራት፣ በብቃትና በጥብዓት ከተዘጋጀ ሌላው ዕዳ ገብስ ነው።

ትዕግስት የሚጠይቀው፣ በብዙ ድካምም የሚሠለጥነው ከምንም በላይ ዋጋ የሚያስከፍለው እነዚያን አባወራዎች ለትውልድ መድኃኒት እንዲኾኑ ማግኘት ማሠልጠኑ ላይ ነው።

ትንሿ ከእነርሱ፣ ጥቂቷ ከብዛታቸው፦ ወግ ኾኖ ለበዛው፣ በዝቶ ላጥለቀለቀን፣ አጥለቅልቆ ሊጠራርገን፣ አጥረግርጎም ወደ ባርነት ሊያግዘን ላለው አልጫነት ፍቱን መድኃኒት ናቸው!

እነርሱን እውነት በኾነ እውቀት፣ የዐለምን ድሪቶ በሚያራግፍ ፈተና፣ በጽናትና ጥብዓትም በሚገነባቸው መከራ መሥራት ቀድመው ለተገኙት አውሪዎች ሳይኾን መኾኑን ለሚናፍቁ አብሪዎች አርአያ ይኾናል።

የማይኖሩትን ጀግንነት፣ የሚኖሩትን አልጫነት፦ ባፍና መጣፍ፣ በመድረክና በዩቲዩብ የሚግቱን እነርሱ፤ የእነርሱ ቢጤ ወሬኛ፣ ሸቃላም ምንደኛ ቢያፈሩ እንጂ ሰውነቱን አውቆ ሠልጥኖበትም ለአልጫዋ ዐለም ጨውነት፣ ለበሽተኛዋም ዐለምም መድኃኒትነት ራሱን የሚሰጥ አባወራ አይወጣቸውም! ተዛዝኖ፣ ተዛዝሎ፣ ማላዘን መነፋረቅም እንጂ!

አባወራዎቹን በጥበብ በጥራትን እንሠራቸዋለን! የመድኃኒት ጥራቱ እንጂ ብዛቱ በሽተኛን እንዳያድነው፤ በዐለም ለበዛ አልጫነትም መሳ ለመሳ የኾነ አባወራነትን አይገድም!

አባወራ

18 Nov, 08:09


ድመት ልጆቿን እንደምትበላ እናት ቤተክርስትያንም ትበላለችን
======================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ባለፉት ሳምንታት ባቀረብኳቸው መረጃዎች መሠረት ቤተክርስትያን (የኢኦተቤ) በልማትና ክርስትያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን አማካኝነት የታተሙ ትውልድን ገዳይ፣ ወንዶቻችንን አምካኝ፣ ሴቶቻችን አሳማጭ መጻሕፍት እንደመጡ ነግሬያችኋለሁ።

በተጨማሪም በ2017 ዓ.ም. በስፋት በዜና፣ በፊልም፣ በዘፈንና በሌሎችም መልኩ እንሰማዋለን ብዬ የነገርኳችሁን የሴቶች ጥቃት፣ አስገድዶ መድፈር፣ የሴቶች እኩልነት፣ የሴቶች ወደ አመራር መምጣትና መሰል ወሬዎችን አስታውሱ።

እንዲሁም ደግሞ እነዚህን "በሴቶች ተቃጣ፣ ይቃጣል፣ ሊቃጣም ምቹ እድል ፈጥሯል" ያሉትን "ሊያጠፉበት"፤ በተለይ ምዕራባውያን ትውልዳቸውን በዘመናዊነት ስም እጅግ የተዋረደ ወራዳ አድርገው ያጠፉበትን፤ የእኛ ትውልድ ደግሞ በባርነት ለማስገበር እንቅፋት የኾነባቸውን ሥርዓት፣ ባህል፣ ወግ ይንዱበት ዘንድ መፍትሔ ብለው ያዘጋጁትን፦ መመሪያ በእናት ቤተክርስትያን በኩል መምጣቱን አስተውሉ!

ስለ ቤተክርስትያን፣ ስለ ሀገር እና ስለ ትውልድ፣ ስለ ልጆቻችሁም እንቅልፍ የማይወስዳችሁ ሰዎች ካላችሁ(ካላችሁ ነው አብዛኛው ሰው ባፉ የሚያወራ ሸቃላና አስመሳይ እንደኾነ እየተረዳሁ በመምጣቴ) በከፍተኛ ጥንቃቄና ንቃት ይህንን ጉዳይ ተከታተሉ።

ወንድምዓለም! የምትበላው ምግብ ስታጣ፣ የምታጠባው ወተት ከጡቷ ሲጠፋ፦ ልጆቿን መብላት ለድመት ደመነፍሳዊ ጠባይዋ ነው።

ይህ ጠባይ ግን ለሰው ልጆች እናት ይኾናልን? ይበልጡን ይብሱንስ ልጆቿን ወደ አምላካቸውና ወደ አባታቸው በእውነት፣ በፍቅርና በጽድቅም ልትጠራቸው ላላት ቤተክርስትያንስ እንዲህ መገለጥ ተገቢ ነውን?

ወደድክም ጠላህም አሁን እየኾነብን ያለው ይህ ነው! በተጨባጭ መረጃና ማስረጃ የእንግሊዟ አንግሊካን ቤተክርስትያን ላይ የደረሰው ብሎም ለሀገሪቷ እንግሊዝ የተረፈው ትውልዱን የማለጭ(demoralising the generation) ሸፍጥ በራሳቸው ጳጳሳት መፈጸሙን ከዚህ በፊት ነገርኳችሁ!

የአንገሊካኗ ቤተክርስትያን በጥቂት ባፍጢማቸው በተደፉ ሆዳደር ጳጳሳቶቿ አማካኝነት ለጽድቅ፣ ለዘለዓለማዊ ሕይወት ከማሕጸነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስቅዱስ የወለደቻቸውን ልጆቿን ቅርጥፍ አድርጋ በላቻቸው(አጠፋቻቸው)።

ይህ ደግሞ ምንም ሚስጥር አይደለም፤ የአደባባይ እውነት እንጂ! ዛሬ ልጆቿ በመረንነት ጠፍተዋል፣ ትዳር መመሥረት አቅቷቸዋል፣ ወንድና ሴቱ ዘንድ መተማመን ጠፍቷል፣ ጥቂት ቢጋቡም ለፍቺ ተጣድፈዋል፣ ብዙ ተባዙ የተባለ ዘርን ማስቀጠል እንዲያ በበዙት ልክ ደግሞ ወንጌል የምስራቹን ማዳረስ ጠልተው በርኩሰትና ኃጢያት ጎስቁለዋል።

ቤተክርስትያኗም የሆዳደሮች፣ በአሳታፊነትና በአካታችነትም ወደ አመራር ጭምር በመጡት የሴትና የግብረሰዶማውያን ካህናትና ጳጳሳት የግል ንብረት ወደ መኾን ስትሸጋገር፤ እግዚአብሄርን ፈላጊው ትውልድ ርቋት አድባራቷም ኦና ኾነዋል።

እነዚያው ሆዳደር ጳጳሳትም ከፍተኛ የሰው ልጅ የኪነ-ሕንጻ ጥበብ የታየባቸውን፣ ታሪካዊ አብያተ-ክርስትያናት (ሕንጻዎቹን) የሚሸጡዋቸው፣ ለሙዚየምና ዳንኪራ የሚያከራዩዋቸው ኾነዋል።

የማሰነውም ትውልዷ ይህንን ሁሉ ውርደትና ውድቀት መታደግ እስካይችል ድረስ ፍዝና ድንዝዝ ኾኖ ጥፋት ባርነቱን፣ መከራ ሞትን በጸጋ የሚቀበል ነፈዝ ኾኗል።

ይህ በአንድ ጀንበር አልኾነም። ይልቁንስ ትውልዱን ቀስ በቀስ በድንዛዜ በመሸርሸር የተሠራ የዘመናት ሸፍጥ እንጂ፤ እኛም ጋር ይኸው እየኾነ ነው።

ይኸው ትውልዱ ተፈጥሮውን ጥሎ፣ የትመጣውን ረስቶ ከአባቶቹ በተለይም ከአባቱ የሚለይበትን መንገድ በባርነት ቀንበር ስር ይንበረከክ ዘንድ ትውልዴ ላይ ሊዘሩት ዝግጅታቸውን ጨርሰው ለስምሪት ተጣድፈዋል!

ሥነ-ሥርባር ያለው ሕዝብ ከትውልዱ መካከል አውጥታ ጠንካራ ቤተሰብ፣ ማኅበረሰብና ሀገር አርኣያ በኾኑ እረኞች የገነባች ያፈራችም ቤተክርስትያን፤ ዛሬ የልጆቿ ድኅነት የማይገዳት በጥፋት ጎዳና የምትመራ የምትበላም ኾና በእረኞቿ መገለጧ አሳሳቢ ኾኗል!

ወንድምዓለም! ትውልዱ ፍዝና ድንዝዝ እንዲኾን ይፈለጋልና፤ ተፈጥሮውን እንዲያውቅ፣ ጸጋውን እንዲለይ፣ መክሊቱን እንዲያወጣ እና እንዲያይልበትም አይፈለግም!

አይፈለግምና የትኛውም እንደ አባቶቹ ይበልጡንም እንዳባቱ ኃይለኛ፣ ጠንካራ፣ ደፋር፣ሥልጡንና አሸናፊ የሚያደርገው ተፈጥሮኣዊ ባሕርዩን ኮንኖ እንደጠላው እንዲጥለውም ይማራል።

በእርሱም ፈንታ አሰስነትን በመንፈሳዊነት ስም፣ አልጫነትንም በጽድቅ ስም ይግቱታል። በዚያም ለባርነት የተመቸ፣ የተደላደለ ኾኖ በወዶ-ገብ ባርነት ይጋዛል ይጠፋልም።

ድመትስ ደመነፍሳዊ ጠባይዋ ቢገዳት፣ ምግብ ያጣች ቀን፣ ወተት የደረቃበት'ለት ልጆቿን ብትበላ፤ እናት ቤተክርስትያን ግን የወለደቻቸውን፣ በእውነት ለጽድቅና ለዘላለም ሕይወት የጠራቻቸውንስ ትበላቸው (ታጠፋቸው) ዘንድ ይኾናልን?

የእንግሊዟ አንግሊካን ይህን አድርጋለች! የእኛዋን እናታችንንም ልታስተምር አሰፍስፋለች! ወገኔን ግን ማን ይንገረው! ተነግሮትም የሰማው ለምን ይኾን እንቅልፍ የመረጠው!

አባወራ

18 Nov, 04:54


በአልጫነቱ ለጸናው ሰውነት ወንድነቱ ይርቀዋል!
=======================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

አልጫ በትርጉም እናስታውስ

🚨 አልጫ(1)፦ coward, ፈሪ፣

🚨 አልጫ(2)፦
demoralized, ወኔው የተሰለበ፣ ሞራል ያጣ፣ ጽድቅን ለመሥራት መስዕዋትነት ለመክፈል(ቤዛ ለመኾን) ተነሳሽነት የጎደለው፤
ማንነቱን(ታሪኩን፣ ተፈጥሮውን) የጣለ(የካደ)፣ ግራገብ፣ ዐለም የሰጠችውን ሳይመረምር የሚቀበል፤
ጎስቋላ (በአካልም ኾነ በሥነ-ልቦና)፣ በስሜቱ በሰውነቱ ላይ መሠልጠን የተሳነው ድኩም፤
ባርነት የተስማማው፣ የሚስማማው ከዚህም የተነሳ ዕጣ ክፍሉ የኾነ፣ ወዶ-ገብ ባርያ።

ከትርጉሙ በሁለተኛው እንደምናየው አልጫ (demoralized) የተደረገ ሰው ከሰውነት ተርታ የወረደ፣ ተፈጥሮኣዊ ማንነቱን የተጠየፈ አልፎ ተርፎም የጠላው፣ የሚጥለውም ነው።

እዚህ ላይ ላልጫ ሰው አለመኾን ወይንም (ደግ ልኹንና) ሰው እንዳይኾን የሚከብደው አልጫነቱን አጽድቆ መጋቱ ነው። እውነት ለመናገር ይህን አልጫነቱን ማወቁ ብቻ እርሱን ገፎ አይጥልለትም፤ መገፋት ግድ ይለዋል እንጂ!

የቀደመው እውቀቱ፣ አጽድቆ የያዘው አሰስነቱ እንደማይጠቅም ለመረዳት መገፋት፣ ከግፊቱም የተነሳ ልቡ መሰበር ግድ ይኾንበታል።

በግፊቱ ጽናት፣ በፈተናው ብዛት፣ በልቡ ስብራት ለመዳን ደግሞ አሰስነቱን አጽድቆ የያዘበት ጥብቀቱ፣ የመገፋትን ጥቅም የተረዳበት እውቀቱ ይወስነዋል።

አሰስነቱ ከደምና ስጋው ጋር ተዋሕዶ፣ ካጥንቱ ተጣብቆ ለተጣባው አልጫ ግን ከተኛበት እንቅልፍ(አዚም) የሚነቃበት የልብ ስብራቱ ጉዳቱም ከፍተኛ ይኾናል።

ይህም እንኳ ቢኾን ላስተዋለው፣ አንድም አስተውሎቱ ራሱ ለነቃለት እንጂ ብዙኃኑ ንክር ያለ ምስኪን አልጫ ተስፋ ቆራጭ፣ በቁም ሟች ነው።

ሰው ተፈጥሮውን ረስቶ፣ ሰው ባሕርዩን ጠልቶ፣ ሰው ጸጋውን ጥሎ፣ ሰው መክሊቱን ቀብሮም "ልኹን" የሚለው ሰውነት፤ እንዳው ላፉ "ሰውነት" ይለዋል እንጂ ቅሉ ከእንሰሳነትም አይለው!

ሰው "ሰው" እንዲኾንበት፣ ሰው የኾነበት፣ ሰው የሚኾንበትና ሰው ያደረገው ባሕርዩን፤ ሲቀጥልም እንዲያ የሚገለጥበትን ጠባዕዩን ጥሎ ሰውነት አይታሰብም!

ይህ ማለት እንጨት መጨስ መንደዱን፣ ብረት መቀዝቀዝ መዛጉን፣ ውሃ መርጠብ መፍሰሱን፣ እሳት መንደድ መሞቁን ትቶ በቀደመ ስሙ ለመጥራት እንደመሞከር ያለ ጅልነት፣ ጅላጅልነትም እንጂ!

ወንድምዓለም! በሰውነት ላይ የሚደረበው ማንኛውም ማዕረግ፣ መለዮ፣ መጠሪያ ሁሉ የተሰማራህበትን መስክ፣ የደረስክበትን እውቀት ለማሳወቅ ከሌላው ሕዝብ ለመለየት ቢጠቅምህ ነው።

ይበልጡንም በተለየ ዕውቀትህ፣ ባካበትከው ልምድህ፣ በተገለጠ ጥበብህ፣ በገባኸው ቃልኪዳንህ ከበፊቱ ይልቅ ታላቅ የአገልግሎት መስቀል እንደተሸከምክ ተረዳበት እንጂ!

ለእርሱም ቢኾን ግን መነሻ መሠረቱ፣ መጠበቂያ ውሃልኩ፣ ማስመሪያ ክሩ ሰውነትህ ቢኾን እንጂ የተሸከምከው ማዕረግም ኾነ መጠሪያህ አይደለም!

ተፈጥሮ ሰውነትክን፣ የተሰጠ ጸጋህን፣ የተገለጠ መክሊትህን ቀብረህ፤ አንድም እነርሱን ኮንነህ፣ ጠልተህ፣ ጥለሃቸውም የምትፋንንበት ማዕረግ፣ የምትኩራራበት መጠሪያ ሁሉ ከንቱ ነው።

በዚህ ልክ አልጫ ለኾነው ትውልድ ከተፈጥሮው ውጪ ምን ቢማር፣ ምን ቁሳዊ ንበረት ቢሰበስብ፣ ምን ሊቅና ሊቃውንት ቢባል ሰው መኾንን፣ የሰውነት ክብርን፣ የሰውነት ዋጋን አላወቀምና ለባርነት የተሸጠ፣ ራሱንም የሰጠ ወዶ-ገብ ባርያ ይኾናል!

አሁን ባለንበት ጊዜና ዘመን መንፈሳዊ በምንለው እውቀት መርምረን ልናውቀው፣ ልንረዳውን ልንደርስበትም የሚገባውን ሰውነት ከሚያስተምሩን ይልቅ አልጫነትን አጽድቀው ለባርነት የተመቸን፣ የሰጠን እንድንኾን የሚደልሉን ምነኛ በዙ!

ወንድምዓለም! አልጫነትን እየተጋትክ፣ ተፈጥሮኣዊ ሰውነትህ፣ መክሊት ወንድነትህ እየተኮነነ በአልጫነትህ ከጸናህ ሰው አትኾንም!

ብዙዎች ልጆቻቸውን ዶክተር፣ ኢንጂነር፣ ቄስና ወታደር እንዲኾኑላቸው መከራ ዐይተው ያስተምሯቸዋል እንጂ ሰው መኾንን እነርሱ ኾነው "ኹኑ" አይሏቸውም።

እንዲህም አይሏቸውምና፤ አንድም ደግሞ እንዲያ ኾነው አሏዩዋቸውምና ሰውነት ተፈጥሮኣቸውን ሳይኾን ሆድ የሚሞላ፣ ገንዘብ የሚሠራ፣ ዝና የሚዘራ ማዕረጋቸውን፣ መጠሪያቸውን ሲሰበስቡ ይኖራሉ።

አሁን የምናየው የምንመሰክረውም ይኼንኑ ነው። ሰውነት ገደል ገብቷል፣ ተፈጥሮ ተጥሏል በፈንታው ገንዘብና ዝና የሚሠራ ማዕረግ ተሸክሞ ወንድሜ በቁም መሞቱ ወግ ኾኗል!

ታናሼ! አልጫነት ጠላትህ ለባርነት እንድትመቸው የሚያስገድድበት፣ አንተ ያመንካቸው ሆዳደር ምንደኛ "ወዳጆችህ" አጽድቀው እየጋቱህ ወዶ-ገብ ባሪያ የሚያደርጉበት ከተፈጥሮህ የተለየ፣ ከጸጋህ ያልተገናዘበ፣ ከመክሊትህም የማይስማማ ተራነት ከንቱነትም ነው!

በጸናህበት አልጫነት ሰውነት ይርቅብሃል! አንድም ወደ አልጫነት በተጣበቅክበት ልክ ከሰውነትህ ትርቃለህ! አንድም አልጫ ኾነህ በምትኖርበት የትኛውንም ማዕረግና መጠሪያ በሰበሰብክበት ኑሮ ሰውነት ተፈጥሮህ ባንተ ላይ አይገለጥም!

በዚህ ሰው ሳትኾን ባለማዕረግ መኾንን ባስቀደምክበት ሕይወትህ፤ በስጋም ኾነ በመንፈስ ለምትወልዳቸው ልጆህ ሰው መኾንን አላሳየሃቸውምና አታስተምራቸውም!

ነገር ግን ከተለመደውና አውቃለው ከሚለው እብሪትህ የተነሳ ባፍና በመጣፍ "ላስተምራችሁ" ብትልም ልክ እንዳንተው በመድረክ ወጥተው፣ ጥንግ ካባ ላንቃ ደርበው የሚያወሩት፣ የሸመደዱትንም የሚያንበለብሉ እንጂ ሰው ኾነው ትውልዱን ሰው የሚያደርጉ አይኾኑም!

ወገኔ ግን ይህንን መች አስተዋለ!

አልጫነቱን አጽደቀው የሚግቱ፣ የጋቱትን ያንኑ በማሳየት የሚያጸኑ፣ እነርሱ ሰውነታቸውን እንደጠሉት፣ እንደራቁትና እንደጣሉት ሆዳደሮች ኾነው ባፍጢማቸው እንደተደፉ፤ ሰውነቱን የናቀ፣ የራቀና የጣለ ትውልድ እያፈሩ ያጠፉታል እንጂ ሰው አያደርጉትም።

ወንድምዓለሜ! በጸናህበት አልጫነት ተፈጥሮ ሰውነትህ ጨውነት ወንድነትህ አይገለጥምና አልጫነትን አምርረህ ጥላው፣ እውነት በኾነ እውቀትም ገፈህም ጣለው እንጂ!

አባወራ

17 Nov, 04:00


ሳሙናችንን ከለገሃር ወደ ሜክሲኮ በሚወስደው መንገድ ከኖክ ማደያ ፊትለፊት ዘይኑ ኮስሞቲክስ ታገኛላችሁ!

በአነስተኛ ዋጋ ድንቅ ጥራት ብቃት ብርካቴም ያለውን ሳሙና ለእርሶና ለቤተሰብዎ አቅርበልኖታል።

ገላዎን፣ ፊትዎንና ፀጉርዎን እጅግ ጥራት ባለው ሳሙናች ይታጠቡ ጤናዎትንም ይጠብቁ!

አባወራ

17 Nov, 04:00


ይህን ድንቅ ሳሙና በመግዛት ሥራችንን መደገፍ ትችላላችሁ!💪

አባወራ

16 Nov, 04:34


ለአልጫ ሕይወት አልተጠራንም!
====================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

አባታችን በቀደመበት አባቶቻችንም ተከትለውት ባሳዩን ጠባቧ መንገድ የእርሷ ሳንኾን ከእርሷ ከተጠራንለት ዓለም መራሩን በእውነት፣ በፍትሕና በጽድቅም ማጣፈጫ ልንኾን እንጂ አልጫ ኾነን እንድንጣል አልተጠራንም።

ጨው እንድንኾን የተጠራን እኛ ጨውነት ባሕርያችን አጣፋጭ ተፈጥሮኣችንን ንቀን፣ ጥለን እና ጠልተን በምንኖረው ሕይወት አልጫነት ዐዲስ ማንነታችን ይኾናል።

አልጫ በኾነ ማንነታችን ዐለም ራሷ የምትንቀን፣ የምትጥለን፣ የምትረግጠንም ሲኾን በዚህ ደግሞ ቀድሞውንም ፈተና በማያጣት ዐለም መገፋታችን ተስፋ አስቆራጭ ይኾናል።

ነገር ግን የጠራን ከእኛ ጋር ያለው እርሱ በዓለም ካለው ይበልጣልና በእርሱ ተስፋ ልንቆርጥ ተሰናክለን ልንወድቅ፣ ወድቀንም ልንቀር አይገባንም። የተጠራንለትም ሕይወት አልጫነትን አይፈቅድም።

ተስፋ መቁረጥ የሚበረታብን፦ ከጠራን ከእርሱ ይልቅ ዐለምን ስለምንሰማ፣ የጠራንን እርሱን ሳይኾን ወጀቡን ስለምንፈራ፣ በጠራን በእርሱ ላይ ካለን እምነት በዐለምና በውሸቷ ስለምንታመን ነው።

አንድም የምናነበውንና የምንሰማውን የአባታችንን ማንነት ከተረትና ከታሪክ እኩል የምንቆጥረው መኾናችን፤ እንዲሁም የሚነግሩንንና የሚያስተምሩንን ጀብድ በማይነኩት፣ በማይሞክሩትና በተግባር ተገልጠውበት በማያሳዩን የመሰበካችን ውጤት ነው።

አባታችንና አምላካችን ግን በዘመናት የማያረጅ፣ ዘመናትና አዝማናትን አሳልፎ የሚኖር "ድንቅ መካር፣ ኃያል አምላክ፣ የዘለአለም አባት፣ የሰላም አለቃ" መኾኑን ምን ያክሎቻችን እናስተውላለን!

ባፍና በመጣፍ ልናወራው እንችላለን፣ በመድረክና በዩቲዩብም ልንሰብከው እንችላለን። ነገር ግን ማጉረምረም በተለየው ልጅነት እንዲህ ዓይነት አባት እንዳለን በሕይወታችን መስክረናልን?

ሕይወታችንን የሚያዩ፣ የቀደመ ታሪካችንን አሁን ካለንበት አቋም፣ ከምናልፍበት መከራስ ዐይተው "እርሱስ 'ድንቅ መካር ኃያል አምላክ፣ የዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ' የኾነ አባት አለው" ብለው የሰማዩ አባታችንን ያከብራሉን?

ወንድምዓለም! አባታችን ለአልጫ ሕይወት አልፈጠረንም! በይበልጥም የእኛን ስጋ ተዋሕዶ፣ በእግሩ ተመላልሶ አርኣያ ኾኖ ባሳየን ቤዛነቱ ለአልጫ ሕይወት አልጠራንም!

ኾኖም ግን ጨውነት ተፈጥሮኣችንን፣ አጣፋጭ ጸጋችንን፣ ዐለምን በእውነት፣ በፍትሕና በጽድቅ ማቅኛ መክሊታችንን አጥተናል። ትኩረታችን የፈተናው ብዛት፣ የመከራው ጽናት፣ የወጀቡ ብርታት፣ የማዕበሉ ቁመት፣ የሞገዱ ጩኸት፣ የጥይቱ ፉጨት ላይ እስከኾነ ድረስ ተስፋቆርጠን ለአልጫነት ለባርነትም መሰጠታችን አይቀርም።

ነገር ግን ዐይኖቻችን ፍርሃታችንን ካራቀበት፣ ሕይወታችንን ካደሰበት፣ ስብራታችንን ከጠገነበት መስቀሉ፤ ተስፋና እምነት ይበልጡንም ፍቅሩን ከሰማንበት ቃሉ ከተተከሉ ጨውነት ተፈጥሮአችን ይታደሳል።

በዐለም ሳለን መከራ እንዳለብን ሲነግረን የሚገጥመንን አስቀድሞ ማሳወቅ ማስጠንቀቁ፣ ማንቃት ማዘጋጀቱ እርሱንም እንኳ ማሸነፉን ለማስረገጥ እንጂ የፈተናው ብዛት፣ የመከራው ጽናት ላይ አተኩረን፦ ስንቆጥር፣ ስንዘረዝርና ስንመዝን ከዚያም የተነሳ በስጋት እንድንኖር አይደለም።

ይልቁንስ ተፈጥሮኣችንን አውቀን፣ የሰጠንን ጸጋ ቆጥረን፣ መክሊታችንን አውጥተን፤ በጠራን በእርሱ በደስታ ተሞልተን በድፍረትና ጥንካሬ አይለን በተፈጥሮኣችንም ላይ ሠልጥነን ወደ ተጠራንለት ልዕልና እንድንወጣ እንጂ!

ታናሼ! ለአልጫ ሕይወት አልተጠራንምና ጨውነት ተፈጥሮኣችንን አንጣል! ብዙዎች አልጫ ኾነን እንድንወድቅ፣ ሰዎች "ጠጠር ናቸው" ብለው እንዲጥሉን፣ በባርነት እንድንረገጥም አልጫነትን አጽድቀው ያስተምራሉና።

"በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?" መጽ ኢያ ፩፥፱

ይህ ኃይለ ቃል ምክር አይደለም ትዕዛዝ እንጂ!

የምወድህ ታናሼ! ጠላት ይበልጡንም ደግሞ ሆዳደር ምንደኞች ዐለምን በእውነት፣ በፍትሕና በጽድቅ የምታጣፍጥበት ተፈጥሮኣዊ ጨውነት-ወንድነትክን እንድትጠላ፣ እንድትጥልና እንድትጣልም አልጫነትክን አጽድቀው ጨውነት-ወንድነትክን ኮንነው ይግቱሃል።

የሚወድህ፣ የሚወልድህ፣ የፈጠረህ፤ ሞቶ ያኖረህና የሚያኖርህም አባትህ ብቻ ስንፍናህን ወቅሶ፣ ድክመትህን ነቅሶ በሕይወት በምትኖርበት ድፍረት፣ ጥንካሬና ሥልጣኔውም ትቆም ዘንድ ያዝዝካል!

ታናሼ! ጠዋት ስትነሳ ዐለምን ለማጣፈጥ የተፈጠርክ፣ የተመረጥክ፣ በድፍረትና በጽናት ልትቆም እንዳለህና እንደታዘዝክ የምታም፤ የድንቅ መካሩ፣ የኃያሉ አምላክ፣ የዘላለሙ አባት፣ የሰላሙም አለቃ ልጅ መኾንክ አስታውስ፣ አስተውል። እንዲህ ያለ አባትም አለህና እንደ ልጅነትህ በልበሙሉነት ደረትክን ነፍተህ ተመላለስ!

ፈሪ፣ ስጉ፣ ድኩም፣ ጎስቋላ ተስፋቢስ ኾነህ ባልጫነት እንድትጣልና እንድትረገጥ አለመጠራትክን፤ እንዲያ መኖርን አጽድቀው የሚነግሩክ አልጫ ሆዳደሮች መኾናቸውን አትርሳ!

ወንድምዓለም! ይህንን ሁሉ የምጽፍልህ ከምቾቴ አልጋ፣ ከድሎት ሕይወትም አይደለም! ቢኾንም ግን አባቴ ለአልጫ ሕይወት አልጠራኝምና፤ አልጫ ኾኜ አላዝንም፣ አላላዝንም አልነፋረቅምምና አንተም ልበሙሉ እንድትኾንልኝ እንዲህ አልኩህ!💪

አባወራ

15 Nov, 14:00


ያልጫ ነገር ሲመነዘር
=============
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ማሳሰቢያ፦ ለዚህ ጦማር አልጫ(1) ቃሉ ፈሪ የሚለውን ይወክላል።

ዛሬ አሁን ባለንበት ጊዜና ዘመን እንዲህ አልጫነት፦
🌟 እንደ መንፈሳዊነት መገለጫ ተደርጎ ሳይነገር በፊት፣
🌟 አሰስነት(አልጫ፣ ሰነፍ፣ ሰበበኛና ስሜታዊ) ጸድቆ የጽድቅ በር ቁልፍ ተደርጎ ሳይቆጠር በፊት፣
🌟 ለሆዳቸው ባፍጢማቸው የወደቁ መምህራን ትውልዱን በተለይም ወንዱን እነርሱ የሚኖሩትን አልጫነት ባፍና በመጣፍ በዩቲዩብና በመድረክ ሳይሸቅሉበት በፊት፣
👉 ድሮ በጀግኖቹ ዘመን፣
👉 ጀግና የወለዱት በድባብ በሚሄዱበት ጊዜ፣
👉 ጀግና የወለዱት እናቶች ለሀገር፣ ለቤተክርስትያን፣ ለሚስቱና ልጆቹ መስዋዕት በኾኑት ልጆቻቸው ቀብር ላይ በሚፎክሩበት ጊዜ፣

👉 በዚያን ጊዜ አልጫም ኾነ አልጫነት ጠባይና ግብሩ በማኅበረሰቡ በተለይም በሴቶች ዘንድ እጅግ የተናቁ ነበሩ! በተለይ በሴቶች ዘንድ፤ ለምን? ከወንዱ ጸጋ፣ ከተሰጠው መክሊት ከድፍረቱም ቢሉ የመጀመሪያው ተጠቃሚና አትራፊ እነርሱ ናቸውና!

በነገራችን ላይ ፈሪ ወይንም አልጫ ስንል ለወንድ እንጂ ለሴት አይነገርም! የሴት አልጫ የላትም በድፍረትና በጥንካሬ የተሰጠውን ኃላፊነት መፈጸም፣ ግዴታውን መወጣት ለተሳነው ወንዱ እንጂ፤

አንድም ድፍረቷ፣ ጥንካሬዋ፣ ጀግንነቷ፣ ሞቷን ሞቶ በሕይወቱ የሚያኖራት ቤዛዋ እርሱ አለና ደፋር መኾን አይጠበቅባትምና እንደርሱ የምትኾንበት የምትተገብርበትም ጸጋ አልተሰጣትም!

ወንዱ ዐለምን ያውቅበት፣ ያስስበት፣ ያቀናበትና ለራሱም ኾነ ለትውልድ ምቹ የመኖሪያ ስፍራ ያደርጋት ዘንድ ድፍረት ግድ ሲለው፤ እርሱንም ተግባራዊ የሚያደርግበት ጥንካሬና ሥልጣኔውን ካልገነባ ትርፉ ንዴትና ብስጭት በሽታና ሕመም ሞትን የሚያስከትል ቁጭትም ይኾንበታል!

ስለኾነም ደፋር ጠንካራና ሥልጡን ኾኖ የሚወጣው ወንዱ፣ የሚኾንበትም ምክንያቱ ይኸው ለሚስቱ ለልጆቹም ካለበት ኃላፊነት፣ ግዴታና ከሌላው የማኅበረሰብ ክፍል ለይቶ ከያዘው ሚናው የተነሳ ነው።

ሴቷ በዚህ ውስጥ፣ በእነዚህ ሁሉ የወንዱ ሚና ስር ከልጆቿ ጋር ተጠቃሚ ነች ወይም ነበረች። ካርል ማርክስና የግብር መሰሎቹ ሴቷን እንደ ቀደመው እባብ አታለው፣ ወንዱንም አልጨው ከአንድነታቸው እስኪለዩዋቸው ድረስ።

ስለዚህም ነገር ሴቷ ለአልጫ ወንድ ያላትን ንቀት በእንጉርጉሮም ኾነ በማጉረምረም ትገልጣለች። ምክንያቱም ትውልድን በማስቀጠሉ ረገድ፣ ልጆቿን መስዕዋትነት በሚጠይቀው የአባታቸው(የአምላካቸው) ሕግና ጥሪ በመንገዱ መምራት አይችልምና፤

አንድም ደግሞ እርሷ ደካማዋ ጾታ ኾና ሳለ እርሱ በድካሟ በኩል መቆም የማይችል፣ የሚፈራና የማይፈልግም (እንደዛሬው ወንድ) ከኾነ፦ አስባ፣ አሰላስላ፣ መክራ ተማክራ አይደለም ደመነፍሷ ራሱ ይጠየፈዋል ይገፋዋል እንጂ፤ እናም ለትዳር አትመርጠውም!

ለምን? ወንዱ አልጫ ነዋ! አልጫን በምን አምና ከአባቷ እቅፍ ወጥታ ትከተለዋለች? አንድም ደግሞ ልብ ለሌለው አልጫ ምኑን አምና ልቧን ትሰጠዋለች?

ስለኾነም አልጫ ወንድ በሚያፈራ ማኅበረሰብ ውስጥ ሴቶች ባል ማግኘት ይቸገራሉ፤ አልጫ ወንድ በሚያሳድግ ማኅበረሰብ መካከል ሴቶቹ በወንዱ አይተማመኑም፤ አንድም አልጫነትን፦ ካላንቺ መኖር እፈራለሁ እያለ በዘፈንና በግጥም ማላዘንን በሚያበረታታ ማኅበረሰብ ውስጥ ሴቶቹ የትዳር ጥቅሙ አይታያቸውም!

እንዲሁም ደግሞ አልጫነት በፋነነበት ማኅበረሰብ ውስጥ አባወራነት እርም ሲኾን የተገለጠበትም ወንጀለኛ ይኾናል። ከዚህም የተነሳ ሴቶች አባወራ የማግኘት እድላቸው ሲጠብ፣ አቋም ያለው ወንድ ቀርቶ ሰውነቱም ለማይቆምለት ወንድ ይሰጣሉ፤ አባወራን አግኝተው ቢያገቡም ደግሞ ባልጮቹ ተዋክበው የመፍታት እድላቸው ይሰፋል።

አልጫ ወንድ በሴቶቹ ዘንድ ሊወደድበት የሚችል ተፈጥሮኣዊ ባሕርዩን፣ ወንድነት ጸጋውን፣ ድፍረት መክሊቱን ጥሏልና ሌላ መወደጃ ሲፈልግ የሴቶች መብት ተከራካሪ ይኾናል።

ከካርል ማርክስ ጀምራችሁ እስከ ዛሬዋ ዕለት ድረስ የሴቶች መብት ጠባቂ፣ ተሟጋች ነን እያሉ ሴቷን ከአባቷና ከባሏ የሚለያትን ርዕዮተ-ዐለም የሚያራምዱ፣ መርሐግብር የሚያዘጋጁ ወንዶችን ከተክለ ሰውነት እስከ የሕይወት አቋማቸው ብትታዘቡ ከዚያ ተፈጥሮኣዊ ከኾነው ወንድነት ጎድለው መወደጃ ምትክ የፈለጉ አልጮች መኾናቸውን ትረዳላችሁ።

እናቱን፣ እህቱን፣ ሚስቱንና ሴት ልጆቹን የሚወድማ እርሱ በጎደለበት፣ በደከመበት፣ በጎሰቆለበት፦ የኃላፊነት ቦታው፣ ሊወጣው ባለው ግዴታው፣ ሊጠብቀው ባለው ሚናው፤ በኩል እርሷን ከማስቀደም ይልቅ እርሱ ራሱ እስከ ሞት ታምኖ ይቆምላት ዘንድ ይሠለጥናል እንጂ!

ወንድምዓለም! ዛሬ ወንዱ ተፈጥሮውን መርሳቱ ብቻ አይደለም እኮን ተፈጥሮውን መካዱ፤ ተፈጥሮውን መካዱም ብቻ አይደለም፦ ኃጢያት ያሠራኛል ብሎ ወንድነት ጸጋውን፣ ድፍረት መክሊቱን መቅበሩ ባርነትን ወዶና ፈቅዶ እንዲቀበል አድርጎታል።

በዚህ ላይ ደግሞ አላውቅም ብሎ ከመማር ይልቅ አውቃለሁ ብሎ የሚኖረውን አልጫነት የሚለፍፈው፣ በመድረክና በዩቲዩብ ትውልዱን ለማሳሳት የሚቸኩለው፣ ባፍና በመጣፍ የሚሸቅለው መብዛቱ የአልጫነት ዘመን ምልክቱ ነው!

የሰው ልጅ መንፈሳዊነቱ፣ በመንፈሳዊነቱም አካል ገዝቶ ከሚታየው ቁሳዊው ዓለም ወጥቶ ረቂቁን ዐለም፣ ተፈጥሮውንም ኾነ አምላኩን በገለጠለት መጠን ሲረዳ ፍርሃቱን ያጠፋለታል እንጂ።

አሁን እየኾነ ያለው ግን እንዲህ አይደለም። ልጆቻችን በተለይም ወንዶቹ መንፈሳዊ ትምህርት ቀመሱ ቀሰሙም ማለት የወጣላቸውና የተዋጣላቸውም አልጮች እየኾኑ መምጣታቸውን አስተውሉ።

ይህም ደግሞ የሥነ-መለኮት ትምህርት ተምረናል ቢሚሉትና የምዕራባውያን በተለይም በካርል ማርክስ ብርዝ ሞቅታ ባገኛቸው ይብሳል።

ታናሼ! ተፈጥሮህንና ፈጣሪህን በምትረዳበት መንፈሳዊ ትምህርት አልጫነትን ካተረፍክ፦ ያስተማሩህ፣ የኖሩትን የራሳቸውን አልጫነት እንጂ አባትህም ኾነ አባቶችህ እስከሞት ያደረሳቸውን፣ ትውልድና ሀገር ያቆዩበትን ጥብዓት አይደለም!

ዛሬ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልግ ጊዜ ላይ ደርሰናል! ወንዱ ደፋር፣ ጀግና፣ ጠንካራ፣ ኃይለኛ እንዲኾን አይፈለግም! አይፈለግምና እነዚህ ባሕርዮቹ ይኮነናሉ፤ አይፈለግምና እንዲያ ሊያደርጉት የሚችሉት ልምምዶቹ ከሕይወቱ እንዲጠፉ ከልጅነቱ ጀምረው ያርቃሉ!

ለምን? ጅል፣ ጅላጅል፣ ጅላንፎ የኾነ ማስትሬትና ዶክትሬት ጭኖ ጥቅምና ሆዱን ሲያሳድድ ስለሚስትና ልጆቹ ደፋር ሳይኾን ፈሪ አልጫም የኾነ ትውልድ፤ ጠላት፣ ይበልጡን ደግሞ ሆዳደር ምንደኞች ይፈልጋሉና!

ሳተናው!
አልጫ ትውልድ ከአልጫነት የሚወጣው መጀመሪያ አልጫ መኾኑን ማወቅና ማመን ሲችል ነው! አለበለዚያ አልጫነትን እንደ ጽድቅ እየሰበከ፣ እንደ ክብር እየተጎናጸፈ፣ እንደ ጀግንነትም እየፎከረ በውርደቱ ሊፎልልበት ይሻልና!

አልጫ ያደረጉትን ሰበባ ሰበቦች መደርደርና ሰዎችና ተቋማት ላይ ጣትን መቀሰርም በአልጫነት ለተነከረው ለእርሱ አይታደጉትምና፤ አልጫነቱን ከማጠናከር ውጪ አይበጁቱም!

በፍኖተ አባወራ ሥልጠናችን የእኛ ካልኾነው ፍርሃት-አልጫነታችን ወጥተን ድፍረት-መክሊታችንን የሚያሳውቀንን እውቀት ገንዘብ እናደርጋለን።

አባወራ

11 Nov, 03:42


እነዚህን እያስተዋላችሁ ባጋጣሚ ሳይኾን በዕቅድ በዓላማም የሚፈጸሙ ናቸው
==========================

እነዚህ ሥልጠናዎች በዓላማ፣ በይዘት፣ በሚሰጡባቸው አካባቢ እና በመሳሰሉት ምን የጋራ የሚያደርጋቸው ነገር እንዳለ መርምሩ!

እንደዚህ ያሉ ሥልጠናዎች በየአጥቢያችሁ በዚህ ዓመት ተጠናክረውና ተበራክተው እንደሚመጡም ጠብቁ!

አባወራ

09 Nov, 03:14


ቤተክርስትያን የምዕራባውያን ጥራጊ መጣያ አትኾንም
=================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ዐይናችን እያየ ጆሯችንም እየሰማ በደምና ባጥንት ዋጋ የተቀበልናትን ቤተክርስትያን የምዕራባውያን ጥራጊ መጣያ ስትኾን እንዴት ዝም እንላለን?

እነርሱ የወደቁበትን፣ እነርሱ መረን የወጡበትን፣ እነርሱ ከአባታቸው የራቁበትን፣ እነርሱ ቤተክርስትያናቸውን ባዶ ያስቀሩበትን፣ እነርሱ ማኅበረሰባቸውን ትውልድ አልባ ያደረጉበትን፣ እነርሱ ትውልዳቸውን አሰስነትን አጽድቀው ሴቷን አመጸኛ ወንዱን ጅላጅል ሞገደኛ አድርገው ያለጩበትን፤ የካርል ማርክስን ሸፍጥ ጠርገው የሚጥሉበት ጉድጓድ አንኾንም።

ትሰሙኛላችሁ ቤተክርስትያን በጾታዊ ጥቃት፣ በእኩልነት ሰበብ፣ ሴቶችን ወደ አመራር በማምጣት ፈሊጥ ክርስትያኑን ማኅበረሰብ አልጫ ልታደርጉት አሰስነትን ልትግቱት ለተዘጋጃችሁ እናንተ!

በተለይም በኑሮ ድህነት፣ በጦርነት እልቂት "ተፈጥሮዬን አልተውም፣ ጸጋዬን አልጥልም፣ መክሊቴን አልቀብርም፣ ወኔዬን አልሰጥም" ያላችሁን ማኅበረሰብ በግራ ጎኑ(በሴቷ) በኩል መጥቶ ለማንበርከክ መሞከር፤ እባብነት ሲኾን ይኸውም ስለቀደመው እባብ ባፍና በመጣፍ እያስተማሩ በግብርም መምሰል ነው።

በ"ኪነጥበብ" ስም ትውልዴን በሽርሙጥና ያጠፉት ሳያንስ በእኩልነት ስም ጭራሽ ዘር እንኳ እንዳይቀርልን ለተኩላ ሊሸጡን የሚያስማሙን፦ እንዲጠብቁን አደራ የተባሉት እረኞች መኾናቸው ያሳዝናል።

ወንድምዓለም! እንግሊዝንና የእንግሊዝ ቤተክርስትያንን ለሴቶችና ግብረሰዶማውያን ክህነት ጵጵስናም የዳረጓት ባፍጢማቸው የተደፉ፣ ትውልዱን ጹሙ እያሉ የሚገድፉ፣ ሆዳደር እረኞቻቸው ናቸው።

በእነርሱ ሸፍጥ ሴት ሁሉ ተጠቂ፣ እናት ሁሉ ተበዳይ፣ ሚስት ሁሉ ተገፊ አድርገው የምትታመንበትን አባቷን፣ ባሏንና ፈጣሪዋን እንድትጠላና እንድትጥለውም አድርገው ብቻዋን አስቀርተዋታል።

ብቻዋን የቀረች እርሷንም፦ ለብቻ ቆሞ መቅረት፣ ቀርቶም በብቸኝነት ከድመት ጋር ማርጀት፦ "ነፃነትና ዘመናዊነት ነው" አሏት። የማንም ሳትኾን ማንም የሚጎትታት፣ ቅዱሳንና ንጉሣንን የሚያፈራ ማህጸኗም የማንም በስሜቱ ያልሠለጠነ ሴሰኛ መተንፈሻ ኾኖ በነፍስም በስጋ ተጎዳች።

እነዚሁ እዛው በሀገረ እንግሊዝ፣ ድሮ በአባቶቻችን ዘመን እኮ አይደለም፤ አሁን እኛ ባለንበት ጊዜና ዘመን ዛሬም በቦታቸው ሳሉ፣ የሞት ቀስታቸውን እንደያዙ ወደ እኛ ወደ ቤተክርስትያናችንም ዞረዋል።

በልማድ ጾማቸው፤ ሆዳቸውን ማሸነፍ ያቃታቸውን ሆዳደሮች ባፍጢም በወደቁበት ከርሳቸው ተቀጥረው ትውልዱን ለማለጭ፤ ነባሩን ትውፊት ለማውደም (decolonising, deconstracting approach ይሉታል) መጥተዋል።

ቤተክርስትያንም በመዋቅሯ በባለድርሻ ተቋማቶቿም ይህንኑ ትውልዱን የማለጭ ሥራ ተቀብላ ልታስፈጽም እንደ እንግሊዟ አንገሊካን ተፈራርማለች። ፳፻፲፯ ዓ.ም.ም በርካታ "የኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ፣ ጋብቻ... ሥልጠና እና የወጣቶች ተቋም ግንባታ" በየወረዳውና አጥቢያው እንሰማለን።

የሥነ-መለኮት ትምህርት ተምረናል ብለው በሆዳቸው ለተኩላ የተገዙ፣ በምስኪኑ ምዕመን "አንቱታን" ያተረፉ፣ ባፍና በመጣፍ፣ በዩቲዩብና በመድረክ የተትረፈረፉ፤ አሁን አንዳቸውን ብጠራ ብዙ የሚጮኹላቸውን ያፈሩ፣ ነገር ግን ፊታቸው የበጎች እረኛ፤ ኋላቸው የተኩላ ምንደኛ መልክ ያላቸው አሉ።

ጊዜው ሲደርስ በተጠናከረ መረጃና ማስረጃ የስም ዝርዝራቸውን ይዤ እመጣለሁ። ለእኔ ግን ዐይነ ውሃቸውን ሳየው ገና እንኳን ከአባወራ ሞገስ ቀርቶ በወንድነት ቁና የሚጎድሉ፣ በወንድነታቸው በአቋምም ኾነ በቁመና ለትውልዱ በተለይም ለወንዱ ምሳሌ የማይኾኑ መኾናቸውን እታዘባለሁ።

ግን ምን ያደርጋል ወገኔ አባቱን ሳይኾን ሰውና ተቋም አምላኪ እንዲኾን አስቀድመው አልጨውታልና ዐይነ ስቡን ብትቧጥጡትም ዕያየ ገደል ይዘውት እየገቡም እንኳ "በእንቶኔማ አትምጣብኝ" ይሏችኋል። ጭራሽ አምልኮት አድናቆቱን የፕሮፋይል ፒክቸር በመቀየር ይመጣል! ድንቄም አድናቆት! አባቱን ነው እኔን ለማስቀናት!

ሳተናው!
ምን እናድርግ? ይህ እኮ የሶሻሊዝም መልክ ነው! ሰው ከሚጎዳው ባላጋራ፣ ሊያርደው ከሚያሰባው፣ ለተኩላም አሳልፎ ሊሰጠው በሆዱ ከተገዛው ጋር ሲገጥም አልፎ ተርፎም ሲቆምላቸው! ከሀገረ እንግሊዝ ስሕተት መማር ያልቻልን፣ ስሕተቷንም የምንደግም እኛ በሞቷ፣ በውድቀቷ፣ በጥፋቷም ቢሉ እንከተላታለን!

እናንተስ ምን ትላላችሁ?

ግድ የላችሁም፤ እናንተ ችግሩ ያን ያክል አልታያችሁ ይኾናል። ነገር ግን ለእኔ ስትሉ፤ እንዳው አፈር ስኾን ይላል አይደል ያገሬ ሰው!

አፈር ስኾን ጊዜ ወስዳችሁ ተወያዩበት! ይህንንም መልክት የቤተክርስትያኔ ጉዳይ ይገዳቸዋል ለምትሏቸው አድርሱዋቸው! ተመካከሩበት ተማከሩበትም!

ዝምታችሁ ሁሉ ከጠላት ወገን እንደሚደምራችሁ፤ በጥፋቷም እንደሚያስተባብራችሁ አስታውሱ!

አባወራ

08 Nov, 11:08


የወንድነት ልኩ የአባወራ ልሕቀቱ ቤዛነት አገልግሎቱ
===============================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

በተፈጥሮኣችን ላይ እያደግንና እየሠለጠንበትም ስንሄድ ሌሎችን ለማገልገል መፈጠራችን በተለይም በራስነታችን ያለው ሥልጣን በፍቅር፦ ለእውነት፣ ለጽድቅና ለፍትሕ የሚሰዋን መኾኑን እንገነዘባለን።

አንተ በወንድነትህ እያየልክ ስትመጣ የተሰጠህን ጸጋ አውቀህ ሠልጥነህበትም ጽድቅን ትፈጽምበት፣ ፍትሕን ታሰፍንበት እና በእውነትም ትቆምበት የሚጠራህ፤ እርሱን ለመወጣት በመክሊትህ የምታተርፍበት ይኾናል።

ይህን ማወቅ፣ መረዳት፣ መኖርም ካልቻልን ነፍሳችን የምትኖርለትን አንዳች ቁምነገር ፍለጋ መባከኗ አይቀርም። በዚህ ፍለጋም መልካም አርኣያ ካላገኘች የመሰላትን በተለይም ደግሞ ስጋዋን "የሚያስደስተውን፣ የሚጠቅመውንና የሚመቸውን" በማድረግ መባከኗ ያጠፋታል።

ወንድምዓለም! የተፈጠርከው አምስት ሺም ቢሉ ሀምሳ ሺህ ደመወዝ የምታገኝበትን ትምህርት "የእውቀት ጥግ" አድርገህ፤ እርሱንም ለማግኘት እየዳከርክ፣ በልተህ፣ ተዋስበህ፣ ልጆች ወልደህ፣ ጡረታ ወጥተህ ልታልፍ አይደለም።

ከተቀጠርክበት ሥራ በተረፈህም ጊዜ ቲቪና የማኅበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ተጥደህ አጫፋሪና አስጨፋሪ ተመልካችና አግጣጭ ታዛቢ ኾነህ እንድታልፍም አይደለም።

ይልቁንስ ተፈጥሮህን ተረድተህ ዐለም የጎደለችበትን፣ የጎሰቆለችበትን፤ የወጣህበት ትውልድ የደከመበትን ለይተህ ክፍተቱን የሚሞላ ሥራ አገልግሎትም ልትፈጽም እንጂ።

ይህን መሰሉ በፍቅር፦ ስለ እውነት፣ ስለ ፍትሕ እና ስለ ጽድቅም የሚደረግ አገልግሎት ደግሞ ምንግዜም መስዋዕትነትን ይጠይቃል። መስዕዋት ልትኾንበት የማትችለው አገልግሎት አይኖርም፤ ካለም እርሱ እውነትና ጽድቅ አይገኝበትም።

መስዋዕትነትን ሳትፈልግ፦ ከችግሩ ከተለየህ፣ ከፈተናው ከሸሸህ፣ ከመከራው ከተደበቅክ አገልግሎትህ እውነትና ጽድቅ ፍትሕም የሚከብሩበት ሳይኾን ጣዖት የኾነብህን ራስክን ልታከብር የወደድክበት ይኾናል።

በዚህም ደግሞ ከተፈጥሮህ፣ ከአዋቂዋ ነፍስህና ከእግዚአብሄር አባትህ እየተጋጨህ ከምትከስህ ሕሊናህ የተነሳ እረፍት ማጣትህ፣ ከደስታ መራቅህ፣ መባዘን መቆጨትህ መማሰንህም አይቀርም።

ወንድምዓለም! ለኑሮህ የሚኾን ሥራን መሥራት፣ በመጠኑ መኖር፣ አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ(ስፖርት)፣ መማርና ማወቁ፣ መብልና መጠጡ፣ ልመናና ምስጋናው ሁሉ፤ ራስክን ከዐለም የምትደብቅባቸው ዋሻዎች አይደሉምና እንዲያ ልታደርጋቸውም አይገባም።

ይልቁንስ ከእነርሱ የተነሳ ኃይለኛ፣ ጠንካራ፣ ደፋርና ሥልጡን ኾነህ ለተጠራህበት አገልግሎት በእርሱም መንገድ ላይ ለሚገጥምህ መስዕዋትነት ትበቃ ዘንድ ታጥቀኻቸው ወደ ዐለም ትሰማራለህ እንጂ!

ቤተሰባቸውን፣ ማኅበረሰባቸውንና ሀገራቸውን ለመጠበቅ የወጡትን፣ እንዲያ አገልግለው ያለፉትን ቅዱሳኑንም ኾነ ጦረኛ አርበኞቹን ስታይ ስለ ጽድቅና እውነት ፍትሕም ሲሉ መከራን በደስታ ጨለጧት እንጂ ሰበባ ሰበብ እየደረደሩ በካቡት ዋሻ አልተደበቋትም።

ልብ አድርግ! የትኛውም ይጠቅመኛል ብለህ ራስህ ላይ የምትሠራው ሥራ ሁሉ የተጠራህለትን አገልግሎት በብቃት እንድትወጣ የሚያደርግ እንጂ አስንፎና አልጮ የሚወዝትህ መኾን የለበትም።

በዐለማችን፣ በሀገራችን፣ በቤተክርስትያናችን፣ በማኅበረሰባችን ብዙ መስተካከል የሚገባቸው ጉዳዮች አሉ። በምናገባኝ እየሰማህ እንዳልሰማ የምታልፋቸው፤ በምንቸገረኝም እያየህ እንዳላየ የምትተዋቸው ከኾነ ግዴታህን የማትወጣ፣ ለእርሱም የተሰጠህን መክሊት የቀበርክ መኾንክን አስተውል!

ሳተናው!
የወንድነት ልኩ የአባወራነት ልሕቀቱ በድፍረት፣ ጥንካሬና ሥልጣኔ ከደረሰበት ልዕልና የሚገኘው ለትውልዱም ቤዛ የሚኾንበት አገልግሎቱ እንጂ ነው!

ለመሸመት፣ ለማሻመድ፣ ለማሸርገድ፣ ለማጨብጨብ፣ ለመዳራት፣ ለማቅራራት፣ ለመታበይ፣ ለመታጀር፣ ለመኮፈስ፣ ለመስገብገብ፣ ለማጭበርበር፣ ለማታለል፣ ለመልፈስፈስ፣ ለመነዳት አልመጣንም።

ይልቁንስ በሠለጠንበት ጸጋችን በመጠን በመኖር በእውነት፣ በጽድቅና በፍትሕ ከምናገለግልበት የፍቅር አደባባይ ላይ ለምንጎነጫት ቤዛነት የጨከነው አርአያችንን ልንከተል እንጂ!💪

ወንድምዓለም! የምትኖረው ኑሮ፣ እየመራኸው ያለውም ሕይወት ከእንሰሳት በምን ይለያል? አብነት የኾኑህን የቀደሙትን አባቶችክንስ በምን ይመስላል?

አባወራ

08 Nov, 06:24


https://youtu.be/VbB_DX2efGQ?si=KfaYOXWTiXWJbF-r

አባወራ

07 Nov, 17:07


አልጫነትን አልወረስንምና አልጫ ትውልድ አናሳድግም
==============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

የሶሻሊስት ርዝራዥ በኾኑ የትምህርት ሥርዓቶች ታፍነው ልጆቻችን ምን ቢማሩ፦ ፈሪ፣ ደካማ፣ ጎስቋላ፣ ጅልና ጅላጅል ኾነው ሆዳቸውንና ጊዜያዊ ጥቅማቸውን እያሳደዱ እንዲያድጉ መፍቀድ የለብንም።

እውነትን የሚሹ እውነት የኾነችውን እውቀት የሚያስሱ፣ ተፈጥሮኣቸውን አውቀው፣ ፈጣሪያቸውንና አባታቸውን ፈርተው ወደ ጽድቁ የሚዘረጉ እንጂ።

ጠላት ይበልጡንም ደግሞ የጠላት ምንደኞች የኾኑ የእኛው "ጉዶች" አጽድቀው ከሚግቷቸው አልጫነት ልንታደጋቸው ይገባል።

ስለኾነም በሚወዷቸውና አባታቸው በሰጣቸው አባቶቻቸው አማካኝነት የመከራን ጣዕም፣ የፈተናን ጥቅም ጥቂት በጥቂቱ እየተለማመዱ እንዲልቁ እናሳድጋቸዋለን።

ተራራ ወጥተው ወርደው፣ ወድቀው ተነስተው፣ ተግጠው ደምተው በዚያው በወጡበት ዱሩ፣ በቁሩ ማደርን እናለማምዳቸዋለን እንጂ ያልተሰጣቸውን ፍርሃት እየዘራንባቸው ለባርነት አንተዋቸውም።

በደኅናው ቀን ከአባቶቻቸው ጋር እንዲህ ከተለማመዱ በክፉ ቀን ስለሆዳቸው ሲሉ ራሳቸውንም ኾነ ሌላውን፣ እምነታቸውንም ኾነ እውነትን የማይሸቅጡ "ሰው" ይኾናሉ እንጂ ሆዳደር ሙሰኛ አይኾኑብንም።

ከእነርሱም ሀገር፣ ቤተክርስትያን፣ ማህበረሰብና ቤተሰብ የተጠሙትንና የተራቡትንም እውነተኛ መሪ፣ እረኛ ራስም የሚኾን ወንድ፤ እርሱንም በመክሊቷ የምትራዳውን ሴት እንጠብቃለንና።

አልጫነትን አልወረስንምና አናሳያቸውም፤ ሆዳደር አልጫ ትውልድም አሳድገን፦ የአባቶቻችንን ትውፊት አናጠፋም፤ የታሪክ ተወቃሽ፣ የመጪው ትውልድ ማፈሪያም አንኾንም!💪

አባወራ

07 Nov, 11:54


የመጣንበት ትውፊት ሊሰረዝ፣ ሊደለዝና ሊበረዝ
=============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ከዚህ በፊት በለጠፍኳቸው ጦማሮች ላይ እንደጠቀስኩት "በጀመርነው የ2017 ዓ.ም. ለኦርቶዶክስ ክርስትያኑ ትዳርና ግንኙነቱን ቤተሰብ አያያዙንም አስመልክቶ ብዙ ሸፍጥ እንሰማበታለን" ብያችሁ ነበር።

ይህንን ሸፍጥ የሚገልጥ እውነትን ስሰጣችሁ፣ ሳቀብላችሁ ጥሩ ስሜት ሊሰማችሁ እንደማይችል እገምታለሁ። ነገር ግን እንደ በወንድነታችን፣ በአባወራት ባለብን ኃላፊነትና ግዴታችን፣ ወደ ተፈጠርንለት ልዕልና በምናደርገው ግስጋሴያችን፦ ስለ ስሜት አንጠነቀቅም፤ ስለ እውነት፤ እውነትም ስለኾነ እውቀት እንጂ!

የተፈጠርነው ስሜታችንን እያዳመጥን ለማባበል፣ እርሱን እየተከተልንም ለመማሰን አይደለም። ይልቁንስ እንደምልክት አስታዋሽም ተጠቅመንበት ስሌትና አመክንዮን አስቀድመን ፍትሕና ጽድቅ የኾነውን ለመፈጸም እንጂ።

ስለኾነም "ስሜታችንን ጎዳህብን፣ የወደድነውን ጠላህብን" የምትሉና ስሜታችሁ ላይ ተኝታችሁ ለምታላዝኑ ምስኪኖች ርህራሄ የለኝም፤ ሀገሬ ቤተክርስትያኔ፣ ትውልዴ እየጠፋ ነውና። የማንንም ተከታይነትና አድናቆት ፈልጌም አልመጣሁምና አልፈልገውምም።

ጥቅሙ ቢገባችሁ፣ የዐለምን ሸፍጥም ከተረዳችሁስ ኑና የአባወራን ሥልጠና ውሰዱ። የከፋ፣ ባህልና እምነትን የሚያጠፋ ጊዜ እየመጣ ነውና ተፈጥሮኣችሁን አውቃችሁና በልጽጋችሁ ታጠቁ! እወቁበት💪

ወንድምዓለም! ከታች ምስላቸው የተቀመጠው ሦስት መጽሐፎች የልማትና ክርስትያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን በጥቅምት ፲፮ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በአባታችን ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቴዎስ አማካኝነት አስመርቆ ያወጣቸው ናቸው።

የኮሚሽኑ የበላይ ጠባቂ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አባ ሳሙኤል በመጻሕፍቱ ምርቃት ወቅት "እነዚህ መጻሕፍት የተዘጋጁት በአማራ ክልል በ26 ወረዳዎች በ76 ቀበሌዎች ለካህናት ማሠልጠኛ ይኾን ዘንድ ነው" የሚል ግር የሚያሰኝ ንግግር አድርገዋል።

ለዛሬ የሁለቱ መጽሐፍ ዝግጅት ላይ የወፍ በረር ቅኝት እናደርጋለን። ሦስተኛውን መጽሐፍንና ለምን ከክልል ክልል ተለይቶ "ለአማራ ክልል?" ተባሉ የሚለውን በቀጣይ ከአንደኛው መጽሐፍ ጋር ይዤ እመለሳለሁ።

እነዚህ ሁለቱ መጽሐፎች ያው ከዚህ በፊትም እንደነገርኳችሁ በ፳፻፲፯ ዓ.ም. የቢሊዮን ብር በጀቱ የድልድል ፕሮጀክቱ መጠናቀቅን ተከትሎ ከሚመጡት ክንውኖች መካከል ነበሩና ኾነ።

የሁለቱንም መጻሕፍት ይዘትና የአጻጻፍ ዘይቤ ብትታዘቡት እንኳን የኢኦተቤንን አስተምህሮ እና የሥነ-ጽሑፍ ዘይቤ ሊኖረው ቀርቶ፤ አንድ ከቤተክርስትያኗ እምነት ውጪ የኾነ ነገር ግን ኢትዮጲያዊ እንኳን "አዘጋጀው" ሊባል የማይችል ተራ ዝግጅት ነው።

ውስጡ ያለው ደግሞ ከአባቶቻችን፣ ከባህላችን በሃይማኖታችንም ስንቀባበለው የመጣነውን ትውፊት ለማስጣል እንደኾነ በስውርም ቢኾን ራሳቸው ደጋግመው ሲናገሩት፤ በግልጽም ደግሞ ከይዘቱ ትረዳላችሁ።(ዝርዝሩን ራሳችሁ ታዘቡ!)

ዛሬ ስለ አዘጋጆቹ ተቋማትና ግለሰቦች ጥቂት ላካፍላችሁ። መጻሕፍቱ የተመለሱት(ከእንግልጣሩ ወደ አማርኛው) ሕትመታቸውን ካሳካው Tearfund ከተባለና መቀመጫውን በTeddington UK ባደረገ ዐለምአቀፍ የክርስትያን የተራድኦ ተቋም አማካኝነት እ.ኤ.አ. በ2016 እና 2017 ከተዘጋጁ የሥልጠና መመሪያዎች ነው።

ይህ Tearfund የተባለ ድርጅት ደግሞ በደሃ (በተለይም በአፍሪካና በደቡብ ኤዥያ) ሀገራት ውስጥ "ድህነትን እቀርፋለሁ፣ ብልጽግናን አመጣለሁ" እያለ ልሂቃኑን በሆዳቸው ገዝቶ ትውልዱን በእኩልነት፣ በአሳታፊነትና በብዝሃነት ስም ግብረሰዶማዊነትንና የጾታ ግራገብነትን የሚያበረታታና የሚያስፋፋ ድርጅት ነው።

እርሱ ደግሞ ለእኛ ኢትዮጲያውያን፣ በተለይም ኦርቶዶክሳውያን "አስቦና ተጨንቆ" መጽሐፍ አሳተመልን ሳይኾን በሌሎች ሀገራት ከተከለውና ውጤታማ ከኾነበት ትውልድንም በቁም ከሚገድልበት መርዝ አካፈለን እንጂ።

ይህም ደግሞ በፈረንጆቹ ጥቅምት ወር ከተጠናቀቀው፣ ባለ ቢሊዮን ብር ፕሮጀክቱ ድልድል ጋር በጋራ ጥምረት፣ በመናበብና በቅብብሎሽ የተሠራ ነው።

እንዴት? ብትሉ፦

እ.ኤ.አ. በNov 11-12-2022 በድልድል ፕሮጀክትና በእምርታ የምርምር ሥልጠናና ልማት ተቋም አማካኝነት በዚሁ በዐዲስ አበባ በተዘጋጀው ኮንፍረንስ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረገችው፤ እንዲሁም ደግሞ በድልድል የፕሮጀክት አማካሪ ቦርድ አባል የኾነችው ሴት የTearfund program development advisor for gender ኾና ስትሠራ የነበረችው ማንዲ ማርሻል ናት።

እርሷ አሁን ላይ Director of Gender Justiceኾና በተሾመችበት የAnglican Alliance and Anglical Communion፤ የእንግሊዟን ቤተክርስትያን ለሴቶች እና ግብረሰዶማዊያን ክህነትና ጵጵስና በእኩልነት፣ አሳታፊነትና ብዝሃነት ስም በሯን እንድትከፍት ትልቅ ሚና ተጫውታለች።

ከዚህም የተነሳ የእንግሊዝ ትውልድ ከቤክርስትያኗ እየራቀ፣ ቁጥሩም እየተመናመነ፣ ነባሩን እምነት የሚያስተምሩት ካህናት እየተገፉ፣ ደሞዝ እያጡ እነ ማንዲ ማርሻልና መሰል የጾታ ተንታኝና አጥኚዎች ግን ከፍኛ ደመወዝና አበል(£50,000) እያገኙ ቤተክርስትያኗን ባዶ አድርገዋታል።

"አሉ" ቢባሉም ጥቂት ሴቶች፣ ግብረሰዶማውያንና የጾታ ግራገብነት ሰለባዎች ቀርተዋል፤ ትውልዱም ከተፈጥሮውና ከፈጣሪው ርቆ፣ ማስኖም ቀርቷል።

በነገራችን ላይ፦
☀️ Gender Justice
☀️ Social justice
☀️ Racial Justice
☀️ Queer Justice
☀️ Immigration Justice
☀️ Climate Justice
☀️ LGBTQIA+ Justice እና የመሳሰሉትም ፍትሓዊ መደብ እናመጣለን ብለው ጥቂት የተማሩት፣ ነገር ግን ባፍጢማቸው በሆዳቸውም የተደፉት፦ ትውልድን የሚበዘብዙባቸው፣ የሚያደነዝዙባቸው፣ የሚያልጩባቸውና ለባርያ ፈንጋዩ ሥርዓት ገባር ትውልድ የሚያፈሩባቸው ሸፍጠኛ መስኮች ናቸው።

ታናሼ! የድልድል ፕሮጀክት ውጤት ተቋማዊ (institutionalized) እንደሚደረግና ይህንንም የኢኦተቤ ልማትና ክርስትያናዊ ኮሚሽን በዋነኛነት የቤተክርስትያኗን መዋቅር ተጠቅሞ እንደሚያስፈጽም ነግሬክ ነበር።

ይኸው የእርሱ ጅማሮ አንዱ ፕሮጀክቱን ከሀገር እንግሊዝ ኾነው በበላይነት የሚመሩት እነ ማንዲ ማርሻል ከዚህ ቀደም በሌሎች ሀገራት ውጤታማ የኾኑበትን መጽሐፍ ቃል በቃል የጽሑፍ ስር ያለው መስመር እንኳ ሳይቀር ወደ አማርኛ ተመልሶ ቀርቧል። ልብ አድርጉ! ከባህልና ከሃይማኖት ትውፊት ጋር የሚጣረስ ይዘቱን ለእናንተ ትቼ ነው

ከዚህ የሚቀጥለው ይህንን ማስፈጸም የሚችሉ፦
🌟 "ትውልድ የሚገነባባቸው ተቋማት" ግንባታ፣
🌟 የማኅበራትና የካህና ዎርክ ሾፕና ሥልጠና
🌟 በዚህም መሠረት ትውልዱን ለተፈለገው ዓላማ ወዶ ሳይኾን ተገዶ የሚገባበትን መርሐ ግብር ዝርጋታ ናቸው።

እንቢ ብንልስ? "ትዳር እናንተና ቀጣሪዎቻችሁ እንደምትሉት በጋራ ሳይኾን በአባወራ ይመራል፤ የጋብቻ ራስ እግዚአብሄር ሳይኾን የሚስት ራስ ባል ነው"ይላል ብንልስ፤

🌟☀️💫 "ከማኅበረ ካህናቱ ጋር ተነጋግረን ከሰበካ ጉባኤ ውጪ እናደርግሃለን" ይህ ሮሚና ኤስትራቲ በጻፈችው በቤተክርስትያናችንም መምህራን አማካሪነት የወጣ ፊልም ላይ የሚነገረው ነው። ነገ መመሪያ አይኾንምን?

(ዋቢ መስፈንጠሪያዎች በcomment ሳጥን👇)

አባወራ

06 Nov, 09:51


አሁን ዛሬ ከሠላሳ ደቂቃ በፊት ግቡና ስሙት እነማን ናቸው፣ ልምዳቸው፣ እውቀታቸው፣ ተልዕኳቸው...

አባወራ

06 Nov, 04:10


ማሠልጠን ባይችሉ ማኮላሸት
===================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ሀገር፣ ቤተክርስትያን፣ ትውልድ፣ ማኅበረሰብ፣ ቤተሰብም ቢሉ ከፍተኛ የሥነ ምግባርና የሥነ ሥርዓት ዝቅጠት ውስጥ የሚገኙበት ጊዜ ነው።

ይህ ከተማርነው ቀደምት ትምህርት፣ ከወረስነው ትውፊት፣ ከሰማነውም ታሪክ የተለየ፣ የራቀ፣ የወረደና የተዋረደ ኢትዮጲያዊ ያልኾነ መልካችን በተለይ ከአናት አይሎብናል።

እነርሱም ደግሞ በዚሁ የወረደና የተዋረደ ከአናትነታቸው ከማይጠበቅ ሥራ ቢወዘቱ ኃላፊነታቸውን ረስተው፣ ቢዘፈቁ ግዴታቸውን ጥለው፣ ቢሰጥሙ ሌላውን ጎትተው መጣላቸው የምናየው "ጉድ" ነው።

በሀገራችን አሁን ባለንበት ጊዜና ዘመን ይህንን በምጽፍበት ሰዓት እየኾነ ነው። ማጣፊያው አጥሮን ነገ ታሪክም፣ ትውልድም፣ በተለይም ልጆቻችን እንዳይወቅሱን ነገርኳችሁ!

እናንተ ግን ተቋምና ግለሰብ ታመልካላችሁና " ይህማ አይኾንም! እነ እንቶኔን ከእኔ የበለጠ አምናቸዋለሁ! በእነርሱማ አትምጣብኝ! አንተ የምትለው ከንቱ ተራ ተርታ ወሬ ነው!" ትሉኛላችሁ።

ምንአለ በኾነ እና ሐሰተኛ በተባልኩ!

ስለተመኘነው የሚመጣ ስለጠላነው የሚቀር ሳይኾን ክፉንም ኾነ ደግን ምግባር ሥራ ለሠሪው ነው፤ እሾህም ላጣሪው እንደኾነ።

እንደ ነገርኳችሁ ትውልዱን በቀናው መንገድ ቀድመው፣ በተፈጠረበት ጸጋ፣ በተሰጠው መክሊት አይሎ እንዲወጣ አርኣያ ኾነው ማሠልጠን የተሳናቸው እነርሱ የሚኮላሽበትን፣ የሚሰለብበትን ዕቅድ ተቋማዊ አድርገው ለመሥራት ታጥቀዋል!

ከትውልዱ ግን ማን አስተዋለ?!

ይህን መሰሉ ድርጊት በሀገረ እንግሊዝ (እንዲሁም በሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ዘንድ) የነበረ የራሳቸውን ትውልድ በተለይም ክርስትያኑንና ክርስትናውን በማለጩ(demoralize) በማድረጉ ረገድ ውጤታማ የኾነም ነው።

በውጤቱም ትውልዷ ከሰውነት ጸጋው ወድቆ፣ ከእንሰሳት እንኳ ርቆ፣ ከሚወደውና ከሞተለት አምላኩና ከአባቱ ተለይቶ ይማስናል። ሀገረ እንግሊዝም ኾነች ቤተክርስትያናቸው ደግሞ እግዚአብሄርን ረስተው፣ ጥለውና ጠልተው መረን ወጥተዋል፣ የጳጳሳቱ የግል ንብረት በመኾን የግ*ብ"ረሰ*ዶ*ማውያ*ን መፈንጫ ኾነዋል።

ትውልዱን አስቀድመው ፍዝና ድንዝዝ አድርገው፤ በዘፈን፣ በድራማ፣ በስብከት፣ በኑሮ ውድነት አድርገው "አፍዝ አደንዝዝ" ግተውታልና አሁን ሀገራቸው ላይ የሚታየውን ድቀትና ውድቀት መታደግ ተስኗቸዋል!

ይህ እኛም ጋር እየተገለጠ እየታየ ሲኾን ይህም ባጋጣሚ ሳይኾን ኾን ተብሎ በጀት ተመድቦለት፣ ሆዳደር መምህራን ተቀጥረውለት የሚኾን እንጂ!

ትውልዱ አልጫ እንዲኾን ይፈለጋልና አልጫነትን ባፍና በመጣፍ፣ በመድረክና በዩቲዩብ አጽድቀው ይግቱታል! አልጫነትን የመንፈሳዊነት ጥግ፣ የዘመናዊነትም ቁና አድርገው ይለፍፉበታል።

ይህንን አንድም ባፍጢማቸው የተደፉ ሆዳደሮች፣ ስለ ትውልዳቸው ግድ የማይሰጣቸው፣ በጥናትና በምርምር (research) ስም ከውጭ ተቋማት ለሚሰጣቸው ስባሪ ሳንቲም ሲሉ የሚሸጡት "ሊቅና ሊቃውንት" ሲኾኑ።

አንድም ደግሞ ከሞላ ከተረፍ አልጫነታቸው፣ ከእርሱ ውጪ የሌላቸው፣ የማያውቁት፣ በቁም የተገለጡበትን ነገር ግን በ"አውቃለሁ" እብሪት ታጅረው ያንኑ አባቶቻቸውን ይበልጡንም አባታቸውን የማይመስል አልጫነት የሚግቱት እነርሱ!

ትሰሙኛላችሁ፦
🌟 አልጫ እንድትኾኑ ይፈለጋል!
🌟 እደግመዋለሁ አልጫ እንድትኾኑ ይፈለጋል!
🌟 እሠልሰዋለሁ አልጫ እንድትኾኑ ይፈለጋል!

🌟 አልጫ ብቻም አይደለም የወጣለትና የተዋጣለት ፍዝና ድንዝዝ አልጫም እንጂ!

ወገኔ በማትገጽ(ማኅበራዊ ትስስር ገጽ) እየወጣ "ኧረ ምን ዓይነት አዚም ነው የተደረገብን" እያለ ያላዝናል! አዎ! የሚፈለገው አባትህ በአርአያው የፈጠረው ራስክን፣ የሰጠህ ጸጋ መክሊትህን ረስተህና ክደህ እንድታላዝን ይፈለጋልና ይኸው ታላዝናለህ!

በአደራ የተሰጣቸውን እረኝነት ትውልዱን ጠብቀው፣ ተንከባክበው፣ ተፈጥሮውንና ፈጣሪውን አሳውቀው በሰጠው ጸጋ በመክሊቱም በልጽጎበት ፴፣ ፷ እና ፻ እንዲያፈራበት፣ በዚያም አባቱን ይመሰልን ዘንድ፣ ሊያሠለጥኑት የሚገባቸው አካላትና ግለሰቦች ተፈጥሮኣዊ ወኔውን ሊሰልቡ አዚመኛ ኾነው ተማምለዋል!

ሳተናው!
ትውልዱ ከትውልዱም ወንዱ፣ ከራሱ አልፎ ይበልጡንም ለሀገርና ለቤተክርስተያን ሊቆም የሚችለውን አባወራ እኔ "ፊት አውራሪ ናቸው" ከምላቸው ባሕርያቱ(ድፍረት፣ ጥንካሬና ሥልጣኔ) ሊለዩት ሥልጠና ተጀምሯል!

ይህንንም የምታደርገው ራሷ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያንና በስሯ የሚገኙ ተቋማት፣ ማኅበራት፣ የቲዮሎጂ "መምህራን" ነን የሚሉ ግለሰቦችም ጭምር ናቸው(ደግሞ እኮ ለዚህም ክልል ተለይቶለታል)።

በዚህም መሠረት በ2017 ዓ.ም. ከቢሊዮን ብሩ የፕሮጀክት ድልድል መጠናቀቅ በኋላ ትውልዱ ያልቸገረውን፣ ያልበላውን ጊዜውን ያልዋጀውን እከክ ካላከክንልህ ይሉታል።

በዚህ ዓመት በርካታ ሥልጠናዎች፣ ዎርክሾፖች፣ ውይይቶች ተጀምረዋል፣ ይቀጥላሉም፤ ታዘቧቸው። በምን ዙሪያ? በወንድነት፣ በሴቶች ጥቃት፣ በትዳርና ተላጽቆው....

ስማቸውም እንዲህ ይመስላል፦
👉 ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ባል፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ሚስት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ወንድ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ሴት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ወንድነት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ሴትነት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ እጮኝነት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ወላጅ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ አባት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ እናት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ጋብቻ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ትዳር፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ የትዳር መመሪያ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ የትዳር ሥልጠና፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ ሽምግልና፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ የምክር አገልግሎት፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ የልጆች አስተዳደግ፣
👉 እርቶዶክሳዊ አመጋገብ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ አካሄድ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ አስተሳሰብ፣
👉 ኦርቶዶክሳዊ... ኦርቶዶክሳዊ... ኦርቶዶክሳዊ!

"እና ምንችግር አለው? እና ምንችግር አለው?" እንደምትሉኝ እጠብቃለሁ። ነገሩን ወደ ውስጥ፣ ዝርዝሩን በጥልቀት ከመመርመር ይልቅ በስሜት ብቻ "ምንችግር አለው" ማለት አሁን ከወደቅንበት አዘቅት ነው አዙሮ የጣለን።

The devil is in the details እንዲሉ ውስጡን መርምሩ ለትውልድ አንዳች ፋይዳ ያለው ከኾነ፣ እንደኾነ። ይህን ማለት ኦርቶዶክሳዊ ገላጭ ከፊቱ ያስቀደመው ሁሉ ስሕተት ነው ለማለት አይደለም።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የላኩላችሁ ጦማር ሸፍጡን ለመግለጥ ባያንስም በቀጣዩ ደግሞ ያገኘኹትን ግልጥልጥ ያለውን፣ የለየለትን እጨምርላችኋለሁ።

ልብ አድርጉ! ታገለግሉበት ዘንድ በተሰጣችሁ ጸጋ፣ ታተርፉበትም ዘንድ በተቀመጠላችሁ መክሊት እንድትበለጽጉ አይፈለግም፤ አይፈልጉምምና አያሠለጥኗችሁም። ይልቁንስ ለባርነት የሰጠ፣ ለብዝበዛ የተመቸ ትኾኑ ዘንድ እናንተንም ኾነ ልጆቻችሁን ያኮላሿችኋል እንጂ!

አልጨረስኩም ይቆየን እንጂ!

አባወራ

05 Nov, 05:39


ቤዛነትን የመረጠ በድፍረት ጥንካሬና ሥልጣኔ የተሠራ እንዲታደግ
======================

አልጫ ቢያዝን ቢያላዝን ቢነፋረቅ ይህንኑም ቢያጸድቅ እንጂ ለትድግና እንዳይኾን እንዳይበጅ!

https://youtu.be/3J1JsM5x-_c?si=4L2iC3yUgKtkOzyR

አባወራ

04 Nov, 03:55


ወንድሞቼ ይህንንም ስሙት! የምትሰሙትም ለደንታችሁ፣ ለልጆቻችሁ፣ ለሀገርና ለቤተክርስትያንም ስትሉ እንጂ ለሄኖክ እንዳይደለ አስታውሱ!💪

https://youtu.be/2-hiwiMV9f8?si=MnNaZftMBUyJIVGt

አባወራ

02 Nov, 09:37


ትውልድን ለባርነት ያስቧል በተፈጥሮው ላይ ጦርነት ያውጇል
=====================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

በስለት እና በእሳት፣ በሰይፍና በጥይት፣ በዱላና በድንጋይ አስፈራርተው፣ አሳደውና ጎድተው ወደ ባርነት የሚነዱት ትውልድ ቁጭት አንድዶት ቢነሳ ያንኑ የተሳደደበትን መሣሪያ ተጠቅሞ ነፃነቱን ማወጅ ይችላል።

ነገር ግን ተፈጥሮውን እንዳያውቅ፣ እንዳይለይ፣ እንዲጥልና እንዲጠላ አድርገው የሰበኩት የሰለቡትም ትውልድ ግን፤ ባርነቱ ዘላቂ፣ ተገዢነቱ አስተማማኝ፣ ለተመዝባሪነቱም ጠያቂና ጥያቄ የለበትም።

ይህም ሲኾን ይኸው ትውልድ እንዲህ ለባርነት መሰጠቱን፣ መገፋት መደፋቱን ተገዶ ሳይኾን ወዶና ፈቅዶ የሚፈጽመው፤ ለልጆቹም የሚያስተምረው አሳዛኝ ፍጥረት ይኾናል።

አልፎ ተርፎም ከዚህ ባርነት ሊያወጣው፣ የከበደ ሸክሙን አንስቶ ጽድቅና ልዕልና ሊያገኝበት የሚችለውን የለዘበ ቀንበር የሚያሳየውን ሁሉ አሳልፎ የሚሰጥ፣ የሚሰቅልና የሚያሰቃይ የሚገድልም መኾኑ ከታሪክም ኾነ ካለንበት ጊዜና ዘመን እንማራለን።

ወንድምዓለም! እንዲህ ያለው ትውልድን ከተፈጥሮውና ከፈጣሪው፣ ከመክሊቱና ከአባቱ የሚለየው ትምህርት፤ በተለይ እውነትን፣ እውነት የኾነ እውቀትንና ጽድቁንም ሊያስተምሩት ይገባቸው በነበሩት ነገር ግን ባፍጢማቸው ተደፍተው በሆዳቸው ጠላት በገዛቸው ሲፈጸም ተቀባይነቱ ያይላል።

እነርሱ፦ ሆዳደር የኾኑት አልጫ መምህራን፤ ለትውልዱ ፈጣሪው በምድር ሳለ ኃላፊነቱን ይፈጽምበት ዘንድ የሰጠውን ተፈጥሮ፤ አንድም አባት ከቸርነቱ የተነሳ ልጆቹ በወረሱት ሥልጣን፣ ባገኙት ቤዛነት፣ በታደሰላቸውም ልጅነት ሠላሳ፣ ስድሳና መቶም ያተርፉበት ዘንድ የሰጣቸውን መክሊት ይጸድቁበት ዘንድ እንዲቀብሩ በሐሰት ሲያስተምሩ፤ አሰስነታቸውን አጽድቀው ሲነግሯቸው ደግሞ ጽድቅና መንግሥቱን ነፃነቱንም ሳይኾን ባርነትና ሞቱን የሚናጠቋት ይኾናል።

በእነርሱ አካሄድ ክርስትናን የአልጮች ማድረግ፣ ክርስትናም አልጫነትን የሚያስተምር ማስመሰል፣ አልጫነትና ክርስትና፤ ክርስትናንና አልጫነትንም የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ እስኪመስሉ ድረስ ምንደኝነታቸውን ጠብቀው ያሴራሉ ይሠራሉም!

ይህም ሲሳካላቸው እያየን ሲኾን፤ በዚህ አካሄድ ትውልዱ አባቱ የነገረውን የምሥራች፣ አባቶቹ የተከተሉትን የነፃነት ዳና፣ እውነተኛዋንና ጠባቧንም መንገድ እየተወ ለዓለም ሸፍጥ የሚሰጥ የሚተላለፍም ይኾናል።

እነዚህ ምንደኞች ባፍም ኾነ በመጣፍ የሚያስተምሩት፣ ይኽንኑ ሸፍጣቸውን በስውር የሚፈጽሙበትን ሲያዩትና ሲሰሙት ደስ የሚል እንጂ፤ ለትውልዱ ተፈጥሮውን በማወቁ፣ ፈጣሪውን በመፍራቱ፣ ወደ አባቱ በመመለሱና ወደ ቀደመ ክብርና ልዕልናው በመውጣቱ ረገድ አንዳች ፋይዳ ያለውን አይደለም።

በስሜት መጮህናጠማላዘንን ከምስጋና እየቆጠሩ መዝሙር ብለውም እየጠሩ፣ በቁጥር ብዛት መመካት፣ በገንዘብና በታይታ መክበርን የእውነተኛነት ምስክር አድርገው እያቀረቡ፦ ትውልዱን ለታቀደለት የባርነትና የግዞት ኑሮ ያመቻቹታል።

አንዳቸውም ተፈጥሮውን እንዲመረምር፣ እንዲያውቅ፣ እንዲረዳ በእርሱም ላይ ሠልጥኖ፣ ሚናውን ለይቶ፣ ኃላፊነቱን ይፈጽም፣ ግዴታውን ይወጣ ዘንድ ኃይለኛና ብርቱ እንዲኾን አያስተምሩትም።

ምክንያቱም በዚያ መንገድ አባቶቹን ይበልጡንም ደግሞ አባቱን የሚመስልበት ዕድሉ ሰፊ ነውና፤ እንዲያ ሲኾን ደግሞ "የፍርሃት መንፈስ" ስላልተቀበለ ስለ ጽድቅና ፍትህ ስለ እውነትም የሚኖር፣ ሞትንም የማይፈራ ደፋር ይኾናልና ነው።

እንዲህ አይሎ፣ ደፍሮና ቆርጦ የሚኖር ትውልድ ከመጣ ደግሞ ጅራፍ ገምዶ ሆዳደሮችን ከሀገሩ ከቤቱና ከአባቱም ቤት ለማባረር፣ የሙስና መዝገባቸውን ለመበርበር፣ ጠረጴዛቸውን ለመገልበጥ ወደ ኋላ የማይል ይኾናልና እውነቱን ይሰውሩበታል።

ስለኾነም ታናሼ! ተፈጥሮህን እወቅ፣ መክሊትህን ለይ ባወቅከው ተፈጥሮ በለየኸው መክሊትህም ሠልጥን፣ የሠለጠንክበትንም ተፈጥሮ የለየኸውንም መክሊት ተጠቅመህ ኃላፊነትህን የምትፈጽምበት፣ ግዳጅ የምትወጣበት በእርሱም ሠላሳ፣ ስድሳና መቶ አፍርተህ ሩጫህን የምትጨርስበት ይኹን እንጂ!

አባወራ

02 Nov, 07:43


ዐዲስ ምርት ተጨማሪ ስጦታ
=================

ይህ በትዕዛዝ የተመረተ የገላ ሳሙና ነው!
ራሳችን ያዘጋጀነው ንጹህ ከሰል ተጨምሮበት፣ ከሚያውድ የአበቦች ሽታ ጋር የተመረተ የገላም ኾነ የጸጉር ሳሙና።

ልዩ የሚያደርገው ለመጀመሪያ ጊዜ ባለከሰሉን ሳሙና ባለመዓዛም አድርገን ማምረታችን ሲኾን።

ስጦታው ደግሞ አምስት ሳሙና እያንዳንዳቸውን በሦስት መቶብር ስተወስዱ አንድ በነፃ መመሩቁ ነው።

አባወራ

01 Nov, 06:01


https://youtu.be/UGwEd_xllyk?si=iB81xL_g8xKERKPc

አባወራ

30 Oct, 05:33


መታዘሉ ለአቅመቢስ መቀዳደሙ ለአባወራ እንዲገባ
===================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

ምንም እንኳ አልጫም አቅመቢስ ቢኾን ቢባልም ቅሉ፤ እርሱ እውቀት ከማጣት፣ ባወቃት ጥቂት እውቀት ከመታበይ፣ ከናቀው እውነት ከኾነ እውቀት የተነሳ ከመደንቆር፣ አባቱ ከሰጠው ነገር ግን ከቀበረውም መክሊቱ የተነሳ ከመጎስቆል ነውና መታዘሉ ለእርሱ ተፈጻሚ አይኾንም!

መታዘል የሚገባቸው መከራ በኾነችው ዐለም፣ ጦርነት ባወጀችብን ምድር በሕይወት ውጣ ውረዱ በተፈጥሮ ሂደት የደከሙ፣ ያረጁ፣ የታመሙ፣ የቆሰሉ፣ የተጎዱ፣ የተሰናከሉ እንጂ አልጫ፣ ሰነፍ፣ ሰበበኛና ለስሜታቸው ልጓም ማበጀት ተስኗቸወው ለወደቁት አይደለም።

እነርሱን ቢያነሷቸውም፣ አንስተው ቢያዝሏቸውም አሰስነት በሽታቸው አልጫነት ነቀርሳቸው የሚበረታባቸውና የሚሰራጭባቸው፤ ሸክምነታቸው የሚያልም ናቸው።

አንድም ደግሞ እነርሱ መታዘል እንዳለባቸው፣ እንደሚገባቸው፣ እንደሚጠብቁም ሲናገሩ ተፈጥሯዊ ስጦታቸው፣ ዜግነታዊ መብታቸው፣ ስለተገፉ ካሳቸው አድርገው ከወደቁበት የበታችነት አዘቅት ያላዝናሉና።

አንድም ደግሞ "መተዛዘል አለብን" ሲሉ ማዘል የማይችሉ፣ ደካማውን ለማዘል ራሳቸውን የማያበቁ፣ መታዘልን ተስፋ አድርገው፣ መተዛዘልን አጽድቀውና ቀብድ ሰጥተው ለመታዘል የሚጠብቁ አሰሶች ናቸው።

አንድም ደግሞ መታዘል ፈልገው መተዛዘልን ከጽድቅ የሚቆጥሩ እንዲሁም እንደኾነ የሚያስተምሩት እነርሱ፦ በአሰስነታቸው ላይ ጨክነው፤ ትውልድን ወደሚገነባ፣ ትዳርን ወደሚመራ፣ ለሀገርና ለወገን የሚያበራ አርኣያ ከኾነ ወደ ወንድነት ልኩ ወደ አባወራነት ርዕሱ መውጣት አልኾንላችሁ ያላቸው ናቸው።

አንድም እንተዛዘል የሚሉት አሰሶች በሰው ጫንቃ ላይ ኾኖ ከፍ ለማለት፣ በሌሎች ሞት ለመኖር፣ በሌሎች ውድቀት ለመረማመድ፣ በሌሎች መስዕዋትነት ለመቆም፣ በሌሎች ቤዛነት ለመትረፍ የሚፈልጉ፤ ይህንንም ደግሞ የማያከብሩ፣ የማያመሰግኑ፣ ዋጋም የማይሰጡት ራስ ወዳዶች ናቸው።

ወንድምዓለም! በወንዶች ዓለም፣ ወንዶች በወንድነት ቁና በሚሰፈሩበት፣ ሞልተው በሚፈሱበትም ግንባር፣ ወንዶች በጥረት አባወራ በሚኾኑበት ምዕራፍ፦ ማዘል አቅመቢስን እርሱም የታመመን፣ ያረጀን፣የቆሰለን፣ የደከመን ነው!

እንጂማ ይሄ አባቱ የሰጠውን ጸጋ፣ አባቱ ፴፣ ፷፣ ፻ም ያተርፍበት ዘንድ የሰጠውን መክሊት ቀብሮ፣ አሰስነቱን አጽድቆ ሲመጻደቅ በአካልና በሥነ-ልቦናው የጎሰቆለውን፤

👉 ከማማረር፣ ከመበሳጨት፣ ከማዘንና ከማላዘን ውጪ በራሱ ላይ መጨከን የማይፈልገውን፤

👉 ባወቀው እውቀት ልክና ቅጥር ሰፍቶና ተንሰራፍቶ ዋጋ መክፈል የማይሻውን አልጫ ደግሞም አዋቂ ነኝ ባይ እቡይ ማዘል ጽድቅ ሳይኾን እርሱን በማጥፋቱ ሂደት ተሳትፎ ዕዳ በደል ማምጣት እንጂ ነው!

ሳተናው!
በአልጮች ዐለም ጽድቅ ማለት ተዛዝሎ፣ ተዛዝኖ፣ ተላዝኖ፣ ተላቅሶ፣ ተሸካክሞ መሄድ ነው። ይህም ደግሞ እንደ መንፈሳዊነት ይነገራል፤ ይሰበካልም!

ይህ ለባርነት የተመቸ፣ ባርያ ፈንጋዩን በማኅበረሰቡ ላይ እንዲሰለጥን ያመቻቸ፣ እንደ መረማመጃ ርዕዮተ ዐለም ሶሻሊዝምን፤ እንደ መጨረሻ መዳረሻ "ፍጹምም" ምዕራፍ ኮሚኒዝምን ይመስላል።

እውነት የኾነን እውቀት ገንዘብ ስናደርግ፤ አንድም እውነት የኾነን እውቀት ገንዘብ አድርገን ስንኖር፤ አንድም እውንት የኾነን እውቀት ገንዘብ አድርገን በኑሯችን በተለይ ደግሞ በሞታችን ስናከብረው ለአሰስነት ቦታ አይኖረውም።

በአሰስነታቸው የሚኮሩ፣ ከአሰስነታቸው የተነሳ ለሚያላዝኑ፣ ይህንኑ አሰስነታቸውን አጽድቀው ከእርሱ ላለመውጣት የሚጥሩት ተጥለው መቅረትን፣ ቀርተው መረሳትን የሚፈሩ አልጮች ናቸው።

በወንዶች ዐለም፤ እውነት በአመክንዮና በስሌት በከፊል ተገናዝባ ከፊሉን ደግሞ በእምነት ታጥራ፣ በተስፋ ተሰንቃ፣ ከፍርሃት ርቃ በልበሙሉነት እስከ ሞት በምትገማሸርበት ወንዶቹ ሙታናቸውን እየቀበሩ፣ አሰሶችን እየጣሉ፣ አቅመደካሞችን እያዘሉ ወደ ልሕቀቱ የሚፋጠኑባት ችቦ ፋናቸውን፣ ምልክት አርኣያቸውን፣ አብነት ዋናቸውን እያሰቡ እውነት ርዕይን የሚቀባበሉባት ናት።

ወንድምዓለም! ታናናሾችህን ይበልጡንም ወንዶቹን በማዘል፦ ብታሰንፋቸው፣ ብታዘናጋቸውና ብታጎሳቁላቸው እንጂ አትጠቅማቸውም!

በማኅበረሰባችን ድሮ ድሮ ነውር የነበሩ፦ ልመና፣ ሳይሠሩ መብላት፣ እግር ዘርግቶ ማውራት፣ የማይሠራን መርዳት፣ ጤናማ ኾኖ ተኝቶ መብላት ስንፍና ብልሹ ምግባር ይባሉ ነበር።

ዛሬ ከባሕር ማዶ እህት ያለችው፣ ወንድም ያለው ወጠጤ ምንም ሳይሠራ ተኝቶ እየዋለ፣ ግራ ቂጡ ሲደነዝዝ በቀኙ እየተገላበጠ፣ ቲቪና ስልክ ላይ ተጥዶም እያደረ ብር ይላክለታል፣ ልብስና ስልክ ጫማና ሰዓት ይቀይራል።

የሚሠራውም ቢኾን እንኳ "ሥራ ጀምሬያለሁና እርዳታችሁ ይበቃኛል" አይልም። "ደሞዜ አይበቃኝም፣ አልበቃኝም" ሲል ስልክና ሰዓት፣ ልብስና ጫማ ላኩልኝ ሲል መታዘሉን በአጽንዖት ይወደዋል።

አሳፋሪ ነው! እንዲህ ዓይነቱን ወንድ ታዲያ እህቴ፣ ልጄ "ወንድ አገኘሁ" ብላ ብታገባው ለእርሷም ሸክም ለልጆቹም ማፈሪያ የኾነ ዘወትር አባቱንና አምላኩንም ሲያማርር የሚሰሙት መጥፎ አርኣያቸው አሰስ መኾኑ አይቀርም።

ሳተናው!
በወንዶች ዐለም፣ እውነት የኾነችን እውቀት ሰምተን በምንኖርባት ስለእርሷም መራራ ጽዋን በምንቀበልባት ዓለም መታዘል መተዛዘል ለአቅመቢስ እንጂ ለአባወራ ጽድቅን እየናፈቁ እምነትን ይዘው፣ ተስፋን ሰንቀው ወደ ጥሪያችን መቀዳደም የተገባ ነው።

አለበለዚያ እድገት፣ ብልጽግና፣ ልሕቀት፣ ጥንካሬ፣ ድፍረት፣ ጀግንነት፣ ኃይለኝነት፣ ልዕልና፣ ምስጋና፣ እርካታና እረፍት አይገኙም። ይልቁንስ ምስጋናቢስነት፣ ድህነት፣ ምሬት፣ ብስጭት፣ ሮሮ፣ ብሶት፣ ሐዘን፣ ማላዘንና መነፋረቅም ቢያስከትል እንጂ!

ቤተሰብቦቻችሁን፣ ታናናሾችሁን፣ ታላላቆቻችሁንም የምታግዙ፣ የምታዝሉ እናንተ አስተውሉ። ሠርተው ማደር የሚችሉ፣ ለእናንተም ኾነ ለትውልድ አንዳች ቁምነገር ማበርከት የሚገባቸውን ውዶቻችሁን በጎደሉበት፣ በደከሙበት ቦታ መቆምን፣ በትጋት ስላበረከቱት መሸለምን እንጂ አሰስነታቸውን በገንዘብም ኾነ በቁስ አትደግፉላቸው!

ትውልድን መስለብ፣ ትውልድን ማኮላሸት፣ ከተፈጥሮኣዊ ኃላፊነትና ግዴታቸውም ማዘናጋት ኾኖ ዕዳ በደል እንዳይኾንባችሁ አስተውሉ!

ትልቁ ችግር እንግዲህ ያሳደገን፣ በየተቋማቶቻችንና ባሕላችንም ውስጥ የገባ፣ ገብቶም የተነሰራፋው የሶሻሊዝም ዕሳቤ ይህንን መቀበል መቸገሩ ነው!💪

አባወራ

30 Oct, 03:50


https://youtu.be/fh4CHyDQscI?si=oaOtAk9zKF-7eI8P

አባወራ

29 Oct, 04:10


https://youtu.be/U3wYz70TvAQ?si=vtJaQ0kruiPTpnI1

አባወራ

28 Oct, 03:15


ከትውልዱ የጠፋውን ወንድነት ፍለጋ ፫ኛ
========================

https://youtu.be/9sVPf2iVuJc?si=vdkhpi-XwflY2mg2

አባወራ

25 Oct, 10:50


https://youtu.be/eFzzuKSPcQk?si=tj6OUqnMeaDQiJmi

አባወራ

25 Oct, 10:49


የተደገሰልንን የማናውቅ ማወቅም የማንፈልግ እንከፎች ነን!
=======================================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

2017 ዓ.ም. ለፕሮጀክት ድልድል ሠርግና ምላሹ ነው! ፕሮጀክቱ ተጠናቋልና ጌቶቻቸው "እጅ ከምን?" ሲሏቸው የሚያሳዩት ሲጠቀልሉት የነበረው ሴራ ይዘረጋል።

ብዙ የአስገድዶ መድፈር፣ የሴቶች መበደል(በተለይም ኦርቶዶክስ በኾኑ የአማራና የትግራይ ተወላጆች)፣ በቤተክርስትያን የሴቶች ተሳትፎ ማጣት፣ በቤተክርስተያኗ አመራር ውስጥ መዘንጋትና የመሳሰሉትን ዜናዎችና ከማይቀረው መፍትሔያቸው ጋር የምናይበት በዜናም የምንሰማበትም ይኾናል።

ከዚህ በፊት ለተከታታይ የጻፍኩበት የቢሊየን ብሩ የድልድል ፕሮጀክት እ.ኤ.አ. በዚህ በያዝነው ወር ማለትም ኦክቶበር 2024 እንደሚጠናቀቅ ነግሬያችኋለሁ።

የዚህን ፕሮጀክት የጥናቱን ውጤት ተግባሪው ደግሞ የኢኦተቤ ልማትና ክርስትያናዊ ተራድዖ ኮሚሽን እንደኾነ፤ በተራዳኢነት ደግሞ ባለድርሻ የኾኑት ማኅበረ ቅዱሳን፣ እምርታ እና ፍኖት የተባሉ ተቋማትን ጠቅሻለሁ።

ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ አጠናሁት ላለው ችግር የደረሰበትን "መፍትሔ" ተቋማዊ ማድረግ ይገባልና፤ እነዚህ ከላይ የጠቀስኳቸው ተቋማት ትግበራውን በማሳለጡ ሂደት ግንባር ቀደም ይኾናሉ።

በዶክተር ሮሚና ኢስትራቲ የተመራው ይህ ፕሮጀክት ጾታን መሠረት ያደረገውን ጥቃት decolonial approach ተጠቅሜ አስወግዳለሁ ሲል፤ እርሷም ይህንኑ ቃል በተለይ በውጪ ካሉት አጋሮቿ ጋር ስትወያይ የምትጠቀምበት ካፏም የማይጠፋ ቃል ነው።

ይህ ዐዲስና ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የመጣ ቃል ደግሞ UKRI በከፍተኛ ገንዘብ በሚደግፋቸው ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ የተለመደ ነው።

ይኹን እንጂ እነዚህ ጥናቶች በከፍተኛ ገንዘብ መደገፋቸው ሳያንስ ትውልዱን መረን ያወጡ፣ በሴቶችና በወንዶች መካከል መተማመኑን ያጠፉ፣ ለሴቷ መብት እንቆምላታለን በሚል ሰበብ ሴቷን አሁንም ያልጠቀሙ ነገር ግን ጥቂት ግለሰቦችን ያከበሩ መኾናቸውን ሸፍጡ የገባቸው እንግሊዛውያን በቁጭት ይናገራሉ።

በቁጭት መናገራቸው ከረፈደ መንቃታቸው ነው፦
🚨 ትውልዳቸው መረን ከወጣ፣
🚨 በሴትና በወንድ መካከል መተማመን ከጠፋ፣
🚨 የሚያገባና የሚጋባ ከታጣ፣
🚨 ልጅ ወልዶ ዘር መተካት ከተረሳ፣
🚨 ወንድ ለወንድ ሴት ለሴት ከተጋባ፣
🚨 የሴት ክህነት ከተስፋፋ፣
🚨 ግብረሰዶማዊው ከክህነት አልፎ ለጵጵስና ሲመጣ፣
🚨 በቤተክርስትያናቸውን የሚሳለም ጠፍቶ ቁማርና ዳንኪራ ሲመታ... ብቻ ምን አለፋችሁ ብዙ እጅግ ብዙ ከረፈደ ጥቂቶች ነቁ! ነገር ግን አሁንም ብዙኃኑ በድንዛዜ ውስጥ ነውና እነዚያኑ የነቁትን ለምን ትቀሰቅሱናላችሁ እያለ ይበሳጭባቸዋል ያሳድዳቸዋልም፦ ትውልድን ማለጭ አመርቂ በኾነ ውጤት ሲጠናቀቅ (demoraliztion) ይህንን ይመስላል።

ዶክተር ሮሚና ኢስትራቲን UKRI £ 1,287,659.00 (ልብ አድርጉ ገንዘቡ በፓውንድ ነው ያገኘኹትም ከSOAS University ድረገጽ ላይ ነው) ሲሰጣት የፕሮጀክቱ አካሄድ የራሳቸውን ሕዝብ በወዶ ገብነት ለባርነት እንዴት እንዳመጣላቸው ጨርሶ እንዳለጨላቸውም ያውቃልና ነው።

ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ በኦርቶዶክስ ቤተክርስተያናት ላይ ያነጣጠሩ መሰል ፕሮጀክቶችን "የኦርቶዶክስ ማዕከል" የሚል ክንፍ አዘጋጅቶ፦ በማገዝ፣ በማስተናገድ፣ በማበረታታትና ዜናቸውን በማሰራጨት የሚታወቀው የካቶሊኮቹ ዩኒቨርሲቲ ፎርድሃም ነው። እነርሱም ከአመራሩ ጀምረው የእርሷ (የሮሚና ኤስትራቲ ደጋፊዎች ናቸው)!

የእርሱ አፈ ቀላጤ ደግሞ ፐብሊክ ኦርቶዶክሲ የተሰኘው ድረገጽ ሲኾን እነርሱም በዋናነት የሴት ክህነትን በእኩልነትና በተሳታፊነት፣ ግብረዶማዊነትን ባለመኮነን እነርሱንም በመቀበልና በማካተት፣ ጾታ መቀየርንም በማጽደቅ የታወቁ የራሳቸውን ካቶሊካውያንን ባለጩበት መንገድ ኦርቶዶክሳውያኑም ላይ ይህንኑ የጥፋት ቀስት ያነጣጠሩ የተኮሱም ናቸው።

እነዚህን ሁሉ እንግዲህ አንድ ሰሞን ስለ ፕሮጀክቱ ስጽፍ ፎቶዎችን ከእነ ማስፈንጠሪያቸው አያይዤ በቂ ማስረጃ ማስቀመጤን አስተውሉ! የጠየቀኝ የለም እንጂ!

ለማንኛውም የዚህ ፕሮጀክት መጠናቀቅ እርሷ(ሮሚና ኤስትራቲ) አክሱም በነበራት ቆይታ በዳሰሳዬ አገኘሁት ያለችውን ችግር፦

፩ኛ "ትዳር" በሚል ፊልም ሠርታበታለች (ፊልሙን ስታዩት ቀና አሳቢ የሚመስል፣ እንደ ቀደመው እባብ ቅን መስሎ በስሜታዊ ጎናችን የሚገባና የምናስብበትን አአምሮ፣ ሚስቶቻችንና ልጆቻችንን የምናፈቅርበትን ልቦና የምናይበትንም ዐይን የሚቆጣጠር የሚበክልም ቫይረስ ነው!)

፪ኛ ለዚህ ችግር "መፍትሔ" ብላም በንስሃ አባትነት ለሚያገለግሉት ካህናት በጠቅላላው የሚኾን መመሪያ አዘጋጅታለች፣

፫ኛ ወደፊት አስገዳጅ ይኾናል በሚባለው መጋባት ለሚፈልጉ ጥንዶች የሚሰጥም የትዳር መመሪያ እንዲሁ (በዚያ በፈረደበት ጻድቅ ቅዱስ ዮሃንስ ከእርሱ ተረጎምኩ ብላ) አሰናድታለች።

ይህንን ደግሞ ከፕሮጀክቱ መጀመሪያ ጀምሮ የነበሩት ግለሰቦች ቤተክርስትያኗ ይህንን ለመተግበር ኹነኛ መዋቅር እንዳላትና እነርሱንም እንደሚጠቀሙ ቃል ገብተውላታል፤ እርሷም ታውቃቸዋለች!

ለማንኛውም UKRI ለአራት ዓመት የመደበው ያ ሁሉ ብር ማሽነሪ፣ መኪና፣ ብረታ ብረት እንዳልተገዛበት ያውቃልና እንዲሁ በቢላሽ ሲጠፋ የሚመለከተው እንዳይመስላችሁ፤ በሆዳቸው በወደቁት ከእርሱ በተቃመሱት በእኛዎቹ ጉዶችም ባይብስ!

"ትዳር" የተሰኘው ፊልም እርሷ(ሮሚና) ኢትዮጲያ በተለይም አክሱም በቆየችባቸው ጊዜያት ከሰበሰብኳቸው እውነተኛ ታሪኮች ያዘጋጀሁት ነው ትላለች።

ፊልሙን እዩት! እኔ ብዙ የማወጣለት ቢኾን አይደንቅም! ታስቦበት ገንዘብ ተመድቦለት የመጣ ዓለማ አለና ከእነርሱ ፍላጎት ጋር እንዲስማማ አድርጋ ጽፋ አዘጋጅታዋለችና!

ነገር ግን ከእርሱ የታዘብኳቸውን በተለይም የታቀደልንን ዓይነት ሥልጠና የወሰዱ ከሚመስሉት ካህን ንግግር ሁለት ነጥቦችን ላንሳ፦

፩ኛ "የጋብቻ ራስ እግዚአብሄር ነው" ማለታቸውን ይህም ዓላማቸው ልክ እንደ ግብር አባታቸው ካርል ማርክስ የቤቱ ራስ የኾነ ወንዱን ለመስበር እንደኾነ፤

፪ኛውና ምናልባትም ከእነዚህ መመሪያዎች ውጪ እኖራለሁ ለሚል ሰው (ያው ባልየው ነው) ቤተክርስተያኗ ከሰበካ ጉባዔ ጭምር ልታሰናብተው እንደምትችል መናገራቸው ነው። (ከእግዚአብሄርም ልጅነት ትለየው ይኾን? አስቡበት!)

ቤተክርስትያን ከእኛ በላይ አዋቂ ከእኛ በላይ ጠማቂ ከቶ ከየት ይገኛል በሚል እብሪት ምክር አንሰማም ባሉ ጥቂት እረኞች መጥፋቷን፣ ማኅበረ ምዕመኑንም ማባረሯን (አልጫነት ይህ ነው) ከእንግሊዝ ካልተማርን በከፋው በእኛ በተለይም በልጆቻችን ይኾንብናል!

ውርድ ከራሴ!

ሳተናው!
ይህንን እየሰማህ እያነበብክም ኋላ በሞትህ አልጋ ላይ ኾነህ የደረሰውን ጥፋት ስታስበውና በደሉንም ስትቆጥረው እንደሰማህ በድፍረት የመጣው ይምጣ ብለህ ለእርማት አመነሳትህ እሳት ይኾንብሃል!

ያውም በቁም የሚያቃጥል፣ ካንተ ውጪ ለማንም የማይሰማ ሐኪምም የማያውቅልህ ብቻህን ውስጥህን በቁጭት የሚያነድ እሳት!

እንግሊዛውያን አሁን ትዳር አልባ፣ ልጅ አልባ መኾን ብቻ አይደለም፤ ያሉትም ገላቸውን እየተለተሉ ጾታ እየቀየሩ፣ ከተመሳሳይ ጾታ እየተንጠላጠሉ ቢያዩዋቸው ምድር ተከፍታ ብትውጣቸው ይመርጣሉ!
አንተስ? አንቺስ? የልጆቻችን እጣ ፈንታ እንዲህ እንዲኾን ትፈልጋላችሁን?
እጅግ ሲሲበዛ ማፈሪያዎች ነን
ውርድ ከራሴ!

አባወራ

25 Oct, 07:01


አልጫነታችን ወራዳነታችን እንጂ ጽድቃችን አይደለም
=============================

ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

🚨 አልጫ(1)፦ coward, ፈሪ፣

🚨 አልጫ(2)፦
demoralized, ወኔው የተሰለበ፣ ሞራል ያጣ፣ ጽድቅን ለመሥራት መስዕዋትነት ለመክፈል(ቤዛ ለመኾን) ተነሳሽነት የጎደለው፤
ማንነቱን(ታሪኩን፣ ተፈጥሮውን) የጣለ(የካደ)፣ ግራገብ፣ ዐለም የሰጠችውን ሳይመረምር የሚቀበል፤
ጎስቋላ (በአካልም ኾነ በሥነ-ልቦና)፣ በስሜቱ በሰውነቱ ላይ መሠልጠን የተሳነው ድኩም፤
ባርነት የተስማማው፣ የሚስማማው ከዚህም የተነሳ ዕጣ ክፍሉ የኾነ፣ ወዶ-ገብ ባርያ።

ትውልዱ ራሱን አውቆ፣ ማንነቱን ተረድቶ፣ ጸጋውን ጠብቆ፣ መክሊቱን ቆጥሮ ወደ ልዕልናው እንዳያድግ ይፈለጋል።

አንድም ትውልዱን በጽድቅ ስም ከተፈጠረበት ግርማ፣ ከተሰቀለለት ዓላማ፣ ከተሰጠው ጸጋ ሊደርስበት ካለውም ልዕልና ርቆ እንዲኖር ይፈለጋል።

አንድም ትውልዱ ደፋር፣ ኃይለኛ፣ ቆፍጣና፣ ቆራጥ፣ ሥልጡን፣ ጠንካራ፣ አርበኛ ሳይኾን ድኩም፣ አልጫ፣ ጎስቋላ፣ አላዛኝ፣ ነፍራቃ፣ ፈዛዛ... እንዲኾን ይፈለጋል።

ይህንንም ደግሞ በሌላ በምንም አይደለም፤ በጽድቅና በዘመናዊነት ስም አሰስነቱን እየጋቱ በአባቶቻቾን ዘንድ ያልነበረ፣ እነርሱም ያላወረሱን፣ ዐዲስና መጤ በኾነ ትምህረት "ዘመናዊነትና መንፈሳዊነት" እያሉ ይግቱናል!

ሕም!

ይህ እንዲኾን የሚፈልጉት ደግሞ በዋናነት እርሱን እንዲያገለግሉ፣ ወደ እድገትና ብልጽግና ወደ ሥልጣኔውና ዘለዓለማዊ ሕይወትም እንዲመሩት በእርሱ ላይ የተሾሙት ባፍጢማቸው የተደፉ ሆዳደር መሪዎቹ ናቸው።

ጠላት በባርነት ሊነዳው ባለው ሕዝብ ላይ ከሰይፍና ከጥይት ጦርነቱ ይልቅ በአነስተኛ ወጪ የትውልዱን ልቡን፣ ወኔውንና ሐሞቱን በመስለብም ቢሉ በማፍሰስ እጅግ ውጤታማ የኾነን ድል ለጠላት የሚሰጡትም እነኚሁ ሆዳደር እረኞች ናቸው።

እነርሱ ባፍጢም ለደፋቸው ሆዳቸው ሲሉ የሚመሩትን ማህበረሰብ ለማንኛውም የተሻለ ጥቅም ለሚሰጣቸው ጠላት ተስማምተውና አስማምተው ይሸጡታል።

ይህንን ሲያደርጉም ያመናቸውን ሕዝብ እምነቱን፣ የተከተላቸውን ሕዝብ ስብከቱን(ትምህርቱን)፣ የሰጣቸውንም አደራ ጥሪቱን ተገን አድርገው፤ ለጠላት አሳልፎ የሚሰጠውን አሰስነትም አጽድቀው በመጋት ነው።

እንዲህ አድርገው ያለጩት ትውልድ ምን "አውቃለሁ" ቢል እያለም ቢኾን ይጎዳል። ማወቅ እኮ ያውቃል ነገር ግን እውቀት ብለው የጋቱት እርሱን ለባርነት እንዲሰጥ የሚያደርገው መኾኑን አይገነዘብም እንጂ።

አንድም አውቀዋለሁ ያለው እውቀቱ፣ አምነዋለሁ ያለው እረኝነቱ ጭምር እርሱን አሳልፎ የሚሰጥ የሴራ ወጥመድ ውስጥ እንደወደቀ አይረዳምና።

አንድም ደግሞ ከመኑ ሸፍጥ የተለየ የቀደመ አባቶቹን ታሪክ አጥንቶ፣ በቅብብሎሽ የመጣ ትውፊታቸውን ተረድቶ፣ "አውቄ ታጥቄ ልኑርበት" ቢል እንኳ ኮንነውና አስኮንነው ያስጥሉታል እንጂ!

በዚህ መንገድ ሲማር ደግሞ እውነት እንዲፈልግ፣ እውነት የኾነ እውቀትን እንዲሻ ሳይኾን ግለሰቦችንና ተቋማትን አምኖ እንዲከተል እንጂ ገንዘብ አድርጎ የሚሠለጥንባትን እውነት የኾነች እውቀት ሲሻ አእምሮውን እንዳይጠቀም ተደርጎ ይሰለባል።

ወንድምዓለም! አልጫነት ወራዳነት ነው! "ከምን መውረድ ነው?" ቢሉም፦
ከተፈጠርንበት ማዕረግ የመውደቃችን፣
የተሸለምነውን ክብር የመጣላችን፣
ከተጠራንለት ቅድስና የመራቃችን፣
ከተጎናጸፍነው ጸጋ የመለየታችን፣
የተሰጠንን መክሊት የመቅበራችን፤ በእርሱም ፈንታ ሞትና ሙስናን የሚያመጣ ጊዜያው ጥቅማችንን፣ ዝናና ታይታችንን ሆዳችንንም የማስቀደማችን ምልክት እንጂ ሥልጣኔም ኾነ ዘመናዊነት አልያም ጽድቅ አይባልም!

በዚህም ደግሞ ለመጪው ትውልድ ለልጆቻችንም ማፈሪያ እንኾናለን! የምናወርሳቸው ቤትና መኪና፣ የአስኳላ ትምህርቱም ቢኾን ራሳቸውን፣ ታሪካቸውን፣ ማንነታቸውን በናቁበትና በጠሉበት ከኾነ አይጠቅማቸውም!

አርነት የምታወጣ እውነትን ሊነግሯቸው፣ እንደነገሯቸውም ኖረው ሊያሳዩዋቸው የሚገባቸው እረኞቻቸው እነርሱን ለባርነት በመሸጡ ሂደት ቀጥተኛ ተሳታፊ መኾናቸውን ሲያውቁ፤

አንድም ለጥቅማቸው ፈርተው ሊመጣ ያለውን ባርነት እያዩ ዝም ማታቸውን ሲያውቁ ክርስትናቸውን አልጮች መናኸሪያ አድርገው እንደመሸጉበት ሲረዱ፣ ከስሕተት ድምዳሜ እርሱም "ክርስትና ራሱ የአልጮች ነው!" ከሚል በዚህም ከእምነቱ መሸሻቸው አይቀርም!

ይህ ሁሉ ሲኾን ጠላት ጥይት ሳይጨርስ ነገር ግን "...ጥይቱን ጨረሰ፣ ዝናሩን አራገፈ ነገር ግን ቤተክርስትያንን አልቻላትም..." እያሉ ባፍና በመጣፍ በሚደልሉን ባፍጢም በተደፉ፣ ትውልዱን ተስፋ በማስቆረጥ ከውስጥ ወደ ውጭ በሚነዱት ይፈጸማል!

ሳተናው!
አሰስነቱን አጽድቀው በጋቱት ትውልድ በአልጫነቱ ተመጻድቆ ወደ ባርነቱ አዘቅት በራሱ ፈቃድ ይፋጠናል። ለእርሱም ደግሞ ጠላቱ ወደ ሙስናው፣ ወደ ተኩላዎቹም ዋሻ የሚጠራው ሆዳደር እረኛ ሳይኾን ዐይኑን እየቧጠጠ ገደሉን፣ ጸጋ-ልብሱን እየገለጠ መክሊቱን እንዲያይ የሚጎትተው ነው!

ድፍረት በተፈጠርንበት ነፃነት ዐለምን ልናስስ፣ ልንነዳ ልንገዛ የምንሠማራበት፤ የእኛ የኾኑትንም ከጠላት የምንጠብቅበት፣ ወደ ጽድቅ መንገድ በኃይልና በሥልጣን የምንወጣበት ባልፈጸምነው ልክ ደግሞ የምንጠየቅበት መክሊታችን ነው!

አሁን ባለንበት ጊዜና ዘመን ትውልዴ በተለይ ዘመናዊ ትምህርት የሚማረው "የትውልዱ እፍታ" በአስኳላውም ኾነ በመንፈሳዊው ትምህርት ወኔውን የመስለብ ሥራ በተጠናና በተቀናጀ መልኩ ይሠራበታል።

በሁለቱም የትምህርት መስኮች የሚወጣው ትውልድም ወንዱ ደካማ፣ ጎስቋላ፣ ፈሪ፣ ጭምት፣ ግራገብ፣ ተጎታች፣ ታዛዥ፣ ጅል፣ ተቀባይ፣ ተደርጎ ሲወጣ፤

ሴቷ ደግሞ ደፋር፣ ቆፍጣና፣ ወሳኝ፣ መሪ፣ ኾና እየተሠራችን ነው። ይህንን ደግሞ፦

🚨 መንግሥት በፖሊሲው፣
🚨 ከውጪ በዓላማ የመጡት "የግብረሰናይ ድርጅቶች" እና
🚨 ከሁሉም በላይ ግ እጅግ የሚያሳዝነው ቤተክርስትያንና ባለድርሻ አካላቷ(ማኅበራት) ይህንን ማስፋፋታቸው ነው።

👉 ማስረጃ ላላችሁኝ፦ ከራሳችሁ ጀምራችሁ፣ የጠቀስኳቸውን ተቋማት ፍሬዎቻቸውን ተመልከቱ መርምሩም!


ወንድምዓለም! አልጫነታችን ወራዳነታችን እንጂ ጽድቃችን አይደለም! ልናይልበትና ልንበለጽግበት ልንጸድቅበትም ከተሠራልን ሥርዓት ርቀን በቆሞ ቀርነት፣ ዘራችንን መተካት የሚችሉ ልጆች ባለመውለድ፣ በፍቺ፣ ዲቃላ በመጎተት፣ በሽርሙጥናም የወደቅንበት ውርደታችን እንጂ ነው!

በዚህም አደራችንን ቅርጥፍ አድርገን የበላን፤ ልንሠራ የሚገባንን ችላ ብለን ለልጆቻችን የማይገባቸውን፣ የማይመለከታቸውንና ያልተጠቀሙበትን ዕዳ የምናሸክማቸው መኾኑን አስተውል!

እኛ ግን ትውልዱ ደፋር እንዲኾን ይህም ደግሞ አባቱ(አምላኩ) ጠብቆ፣ ተንከባክቦ፣ አሳድጎ፣ ሠልጥኖበትም ሠላሳና ስድሳ መቶም ያማረ ፍሬ የሚያፈራበትን እንጂ ከባርነትነትና ሞት ሌላ ምንም ረብ የማይገኝበትን የፍርሃት መንፈስ እንዳልሰጠው እናሳየዋለን! 💪

አባወራ

25 Oct, 03:37


ድፍረት ልናተርፍበት የሚገባ መክሊታችን ስለመኾኑ
=============================
💪 ድፍረት ለምን ተሠጠን?
💪 ደፋር መኾን ይቀላል ጠንካራ መኾን?
💪 ደፋር ለምን እንድንኾን አይፈለግም?
💪 እነማን ደፋር እንድንኾን አይፈልጉም?
.
.
.
https://youtu.be/JTPPW4p5aX4?si=fQe6PDN5oKJLCqBy

አባወራ

24 Oct, 06:14


ወንድነትን ፍለጋ ፩
==========
https://youtu.be/8llUpWqWOwU?si=T9XdEWfavaST8nSu

አባወራ

23 Oct, 08:10


መክሊት ድፍረቱን ይቀብሯል በባርነት ምሱ ይወጧል
==============================
ሳተናው!

አንድ ወንድምህ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ፣ በልምድም በስሎ ያገኛቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሃል፤ አንተ ግን በወደድከው ኑር!

አባታችንና አምላካችን ለእኛ ለልጆቹ ከሰጠን፣ በተፈጥሮ ካጎናጸፈን ጸጋዎቹ ውስጥ በተለይም ለወንዱ ይበልጡንም ለአባወራው ድፍረት ዋነኛው፣ ቀዳሚውና በመጀመሪያነት ሊመጣ የሚገባውም ነው።

ዋነኛው አልኩኝ ለወንዱም ኾነ ለሴቷ፣ በስጋም ኾነ በነፍስ ከዋና ዓላማቸው ለመድረስ፣ በትሩፋታቸውም ለማትረፍ ቢፈልጉ ፍርሃት በከበባት ዓለም ድፍረት ያስፈልጋቸዋልና ከተሰጧቸው በርካታ ጸጋዎች መካከል ከዋነኞቹ ይመደባልና ነው።

ቀዳሚው አልኩኝ በተለይ ለወንዱ "ወንድ" የሚያሰኘው፣ በወንድነቱ በሴቷ ዘንድ የሚያስወድደው፣ በዓለም ?ተሰማርቶም ኑሮውን የሚያሸንፈ፤ ከዋነኞቹ መካከል ከቀዳሚዎቹም ተርታ ይሰለፋልና፦ ድፍረት ጸጋውን በቀዳሚነት ታጥቆ እንዲያተርፍበት ነው።

በመጀመሪያነት ሊመጣ የሚገባው አልኩኝ ይበልጡን ለአባወራው፣ ወደ አባወራነት ማማ ለሚወጣው፣ እንዲወጣ ለሚሠለጥነው፣ ሊወጣ ላለው፣ ለወጣውም ድፍረትን ቀድሞ የሚመጣ አንደኛ የለምና ከቀዳሚዎቹ የመጀመሪያው እርሱ እንጂ ነው ስል እንዲህ አልኩ!

በአባወራ ሥልጠናችን ትኩረት ሰጥተን የምናነሳው ከዚያም በተደጋጋሚ እያነሳን የምንወያይበት ርዕሰ ጉዳይ ቢኖር ይህንኑ ከትውልዱ፦ የራቀውን፣ ከወንዱ የጠፋውን፣ ከአባወራውም የተለየውን፦
💪 ራሱ፣
💪 ሚስቱ፣
💪 ልጆቹ፣
💪 ቤተሰቡ፣
💪 ማኅበረሰቡ፣
💪 ቤተክርስትያኑ፣
💪 ሀገሩ፣
💪 ዐለሙም ጭምር ይጠቀሙበት የነበረውን ነገር ግን እርሱን ከወንዱ ከማጣታቸው የተነሳ የማሰኑበትን፣ የጠፉበትን፣ የተጎዱበትን ድፍረት ነው።

ትውልድ፤ በተለይም ወንዱ ድፍረትን ታጥቆ፣ አጎልብቶትና በልጽጎበትም እስካልተገለጠ ድረስ ከላይ የዘረዘርኳቸው ሁሉ ከእርሱ አልጫነት የተነሳ ፍዳቸውን መብላታቸው አይቆምም!

"ድፍረትን ታጥቆ" አልኩኝ ከገበያ ገዝቶ፣ ከዐለም ለምኖ፣ ከሰው ተውሶ፣ ከመጽሐፍ አንብቦ፣ ከሰዎች ሰምቶ፣ ከቤተሰቡ ወርሶ፣ ከደፋሮቹ ተዋልዶ የሚያገኘው አይደለም።

ይልቁንስ በተፈጥሮው ከፈጣሪው፣ በልጅነቱም ከአባቱ ያገኘው፣ አባቱና አምላኩ የሰጠው ነገር ግን እውነት በኾነ እውቀት ዐውቆት ተረድቶት፣ በፈተና መዶሻ እየቀጠቀ፣ በመከራ ሞረድም እየሳለ የሚታጠቀው ጠላቱን ማሳፈሪያ፣ ዐለሙን ማሸነፊያ መክሊት-ጦሩ ስለኾነ እንጂ!

"እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንምና።"

፪ኛ ጤሞ ፩፥፯

ወንድምዓለም! ጠላትህም ኾነ የትኛውም ባላጋራህ አንተን ለመርታት ከሚታጠቃቸው፣ ከሚያነሳቸውና ወዳንተ ከሚወረውራቸው የጦር መሣሪያዎቹ መካከል እጅግ ውጤታማው ጦሩ የፍርሃት ጦር ነው።

አንተ እንድትፈራ፣ እንድትፈራው፣ ድርጊቶችህ ሁሉ መነሻቸው ከእውቀትና ከእምነት በፈተና ከታሸም ልምድ ላይ ከሚነሳ ድፍረት ሳይኾን አስቀድመህ በሰማኸውና ባየኸው ተመርኩዘህ በናላህ ላይ ከሳልከው ስጋት ላይ እንዲኾን ያደርግሃል።

ይህንንም በዘመናዊ ትምህርትና በመንፈሳዊነት በሥልጣኔም ሰበብ አድርጎ አሰስነትን አጽድቆ ይግትሃል። ካልነቃህበትም ተሳክቶለት ምን ብትማርና ብታውቅ፣ ሀብትና ሥልጣንም ቢኖርህም ቅሉ እያንዳንዱ ውሳኔህ፣ ንግግርህና እርምጃህ በልብህ ሞልቶ ከፈሰሰው የፍርሃት መንፈስ ይኾናል!

በተለይም ፍርሃትህን ምክንያታዊ አድርገህ፣ የፍርሃትክን ውጤት እርሱም አልጫነትክን ላለማመን ሰበባ-ሰበብ ደርድረህ፣ ይብሱንም ደግሞ እነርሱን አጽድቀህ ስትቀበለው፤ ለእርሱ ለጠላትህ ከፍተኛው ድሉ፤ ላንተም ኾነ ለልጆችህ ደግሞ ከማትነሳበት የባርነት አዘቅት የሚጥልህ ሽንፈትህ ይኾናል።

ለምን ትፈራለህ?

ታናሼ!
አሁን የገጠመን የትውልድ ኪሳራ ይህ ነው!
አሁን የተንሰራፋብን ወረርሺኝ የኾነ በሽታ ይኸው ፈሪነት ነው!
አሁን ከትውልዱ አንጀት ገብቶ፣ ከደምና ስጋው፣ ከአጥንትና ጅማቱ ተጣብቶ ይበልጡንም በአእምሮው ውስጥ በከፍተኛ ፍጥነት እየበዛ፣ እየተባዛና እየተባዘተ ባርነትና ሞት ያመጣብን ነቀርሳ ስሙ አልጫነት ነው!

ተጠንቀቅ ! አልጫነት ወረርሽነትን አልፎ ነቀርሳም(cancer) ይኾናል!

ለዘመናት በዘመናዊነትና በመንፈሳዊነት ሰበብ አሰስነቱን አጽድቀው ባፍና በመጣፍ የጋቱት ትውልድ፤ ድፍረት ጽድቅ ይሠራበት፣ ዐለሙን ያሸንፍበት ዘንድ የተሰጠው ጸጋ መክሊትም እንደኾነ ማስተማር ከክህደት ሊያስቆጥር ይችላል!

መክሊት ድፍረቱን ቀብሮ በነፃነት የሚኖር፣ እውነትን የሚመሰክር፣ እርሷንም የሚኖራት፣ ስለእርሷም መከራን የሚቀበል፣ ከአባቱ ዘንድ ያየውንም ቤዛነት አገልግሎቱን የሚከተል ወንድ ይበልጡንም አባወራ አይኖርምና ባርነትና ሞቱ ዕጣ ክፍሉ ለእርሱም ኾነ ለዘሩ ይኾናል!

ስላወቅከው፣ ስለተረዳኸው፣ ስላመንክበትም እውነት የኾነ እውቀት ለመመስከር፤ በተለይም "ውሸት ነው፣ ጊዜው ተቀይሯል፣ ተክዷል ተረስቷል" በሚሉህ ዘንድ አውቀህ ባመንክበት እውነት ለመኖር ድፍረት ይጠይቃል!

አለበለዚያ በአፍህ አጣፍጠህ፣ በመጽሐፍ ደልለህ የምታቀርበው እውነት የኾነ እውቀት፤ በሕይወት ተወራርደው ሊመሰክሩት፣ ሊገልጡትና ሊሞቱለት የማይገባ የአልጮች ተረት መኾኑን ታዝበው፤ የምትነግራቸውን እየጣሉ ተግባርህን እያዩ የሚያድጉ ልጆችህና ሚስትህ ይንቁታል! አንተንም እንዲሁ!

ዛሬ ትውልዳችን የተጋባበት፣ እግር ከወርች ያሰረውም ፍርሃት የተነገረውን እውነት የኾነ እውቀት ተገልጦበት ኖሮ፣ መስኮሮለት ቆሞ፣ ያመጣለትን መከራ ተጋፍጦ፣ ይህም ደስታው በመኾኑ ታምኖ ያሳየው የለም፤ ቢኖሩም ጥቂቶች እነርሱንም ለማየት አልታደለምና ነው!

እንዲህም የሚል አለ፦
በምትሄድበት ሁሉ አምላክህ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ነውና ጽና፥ አይዞህ አትፍራ፥ አትደንግጥ ብዬ አላዘዝሁህምን?

ኢያ ፩፥፱

ሳተናው!
አትፍራ!

አልጨረስኩም... ይቆየን እንጂ!

አባወራ

22 Oct, 09:22


ትዳርሽ ቤተሰብሽና ልጆችሽ ላይ የታቀደው ጥፋትና መድኃኒቱ
======================================
አንቺ የውብ ዳር!

አንድ ወንድምሽ በፈተና ተንጦ፣ በንባብ ረግቶ በልምድም በስሎ ያተረፋቸውን መራር ሐቆች በምክር መልክ አቅርቦልሻል፤ አንቺ ግን በወደድሽው ኑሪ!

ጊዜ የለንም! ጠላት ጥቂት ባፍጢም የተደፉ፣ በሆዳቸው የተገዙ ምንደኞችን ይዞ፣ የፈዘዙ ብዙኃኑን አስከትሎ መውደቂያ ጉድጓዳችንን እየማሰ ነው።

በተለይ ደግሞ ሀገር የምትገነባበት፣ መሪም ቢሉ መልካም እረኛ የሚወጣበትን ትዳር እንዳይቆም እንዳይጸናና እንዲፈርስም፤ በሴቷና በወንዱ መካከል ጥርጣሬና ውዥንብር በመፍጠር ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ሊነቀንቀው ታጥቋል።

ይህንንም ደግሞ በተለይ ላንቺ መብት፣ እኩልነት፣ ነፃነት፣ ተሳትፎ እቆማለሁ፤ ከጥቃትም እጠብቅሻለሁ ብሎ መምጣቱ የቀደመውን እባብ በመልክ ባይኾን በግብር ያስመስለዋል።

ስለኾነም እህትዓለም! ሊሞትልሽ ካለው፣ እናትና አባቱን ጥሎ ከመጣው፣ ልብሽንም ከሰጠሽው፣ ልጆችም ከወለድሽለት ባልሽ(አባወራሽ) ከነገረሽ በተቃራኒ የሚነገሩ "አውቅልሻለሁ፣ አስብልሻለሁ፣ እጠብቅልሻለሁ" የሚሉ ቃላትን ለመስማት አትቁሚ!

እንዲህ የሚሉሽ እነርሱ ማንም ቢኾኑ አንቺን ከአባወራሽ፣ ከልጆችሽ አባት ነጥለው ፣ ትዳር ቤተሰብሽን አፍርሰው፣ ልጆችሽን መረን አውጥተው በባርነት ሊነዱሽ ያላቸው እንደኾኑ አስተውይ።

ትዳር በተሰኘው አባትሽና አምላክሽ በመሠረተው ጥንታዊና መሠረታዊ ተቋም ውስጥ ሕግና ሥርዓትን ጠብቆ የአባታችሁን ግዴታ የምትፈጽሙበት ተቋማዊ የሥልጣን መዋቅር አለ።

እርሱም አንቺ በፍጹም ትኅትና ራስሽ ለኾነው አባወራ የምትገዢበት በዚያም፦ ቃሉን በመስማት፣ ፈቃዱን በመታዘዝ፣ ያንኑም በመፈጸም የምትከብሪበት ሲኾን፤

እርሱ ደግሞ በፈንታው በተሰጠው የራስነቱ ኃላፊነት አንቺንም ኾነ ቤተሰቡን፦ በመጠበቅ፣ በመገንባት፣ የሚያስፈልጋችሁን በማቅረብ ራሱን እስከ ሞት ድረስ አሳልፎ የሚሰጥበት በዚህም አባቱን የሚመስልበት አገልግሎት ነው።

ከጥቂት ዓመታት ወዲህ ግን የትዳር ትምህርት፣ የጋብቻ ሥልጠና እና ምክር እንዲመክሩ እየተማሩ ያሉቱ፤ ትውልዱ ለባርነት ወዶና ፈቅዶ እንዲገባ፣ ለብዝበዛና ለውደቀት ተላልፎ እንዲመጣ፤ አባቱና አምላኩ ከሰጠው ጸጋ እንዲርቅ፣ መክሊቱንም እንዲቀብር፣ ሚናውን ጠብቆ ኃላፊነትና ግዴታውን እንዳይወጣ እንዲያልጩትም እየተላኩ ነው።

አንቺ የውብዳር!
ሴታቆርቋዦቹ ገንዘብን ከፊት አስቀድመው እርሱን ብለው ባፍጢማቸው የተደፉ፣ በሆዳቸው የወደቁትን ታላላቆቹን ሳይቀር አስተው ለእኔና ላንቺ፣ ለትዳራችንና ለቤታችንም ማፍረሻ መራጃ(ትልቅ መዶሻ) በትዳር መመሪያና ማሠልጠኛ ሰበብ ያዘጋጃሉ ያሠለጥናሉም።

እነርሱም በያዙት ዕቅድ መሠረት ባንቺና በአባወራሽ መካከል ለምክር ሊገኙ የሚገባቸውን የነፍስ አባት(የንስሃ አባት) ተጠቅመው ይህንኑ መርዘኛ ትምህርታቸውን ሊዘሩ ያቅዳሉ።

ለዚህ ሸፍጠኛ ማርክሲስታዊ ተንኮላቸው መፍትሄው፦
፩ኛ የነፍስ አባትሽ ምክር "ምክር" እንጂ ነፍሱን አሳልፎ ላንቺ ከሚሰጠው ገዢሽ ከኾነው አባወራ በላይ አለማድረግ፣ አለማስቀደምም ነው።

ምንም ቢኾን እርሱ የቤቱ አዛዥ፣ ናዛዥ፣ ወሳኝ፣ ሕግ አውጭ ነውና። ብዙ የምወዳቸው ዘመናዊ ትምህርት የተማሩ እህት ወንድሞቼ በዚህ ዓይነቱ ሸፍጥ ተጎድተዋልና እንዲህ አልኩሽ።

፪ኛ ቢቻል እኚህ የነፍስ አባት ሊመክሩሽ፣ ሊያስተምሩሽና ሊባርኩሽ ሲመጡ አባወራሽ ባለበት፣ እርሱ የሚናገሩትን በሚሰማበትና በሚያይበት ይኹን።

ጥቅም የደለላቸው፣ ልወደድ ባይነት ያየለባቸው ጥቂት የማይባሉ ካህናት ላንቺ ያሰቡ እየመሰሉ ባንቺና በእርሱ ፍቅር መካከል ንፋስ፣ በእምነትሽም ላይ ጥርጣሬ፣ በቁስልሽም ላይ ጥዝጣዜ ያመጣሉና ነው።

፫ኛ አንቺ ራስሽ ከምታውቂውና በቅዱስ መጽሐፍ ከተጻፈው ተቋማዊ መዋቅር እርሱም አባወራሽ ያንቺ ራስ መኾኑን፤ አንቺም ልትገዢለት እንዳለሽ ከሚያውጀው የተለየ የእኩልነት፣ የመብት፣ የነፃነት፣ እና የመሳሰሉትን ባዕድ ትምህርቶች ሲቀላቅሉ በግልጽ "ተዉ..." በዪ!

፬ኛ ምንም ይኹን ምን የአካልሽ ክፋይ ከኾነው አብራክሽ አትለይ! ተለጠፊበት! ላትነጠይ ተጣበቂበት! ይልቁንስ ከዚህ በተቃራኒው ከሚመክሩሽ ራቂ እንጂ!

፭ኛ የእኔ የወንድምሽ ምክርም እንኳ አባወራሽ አንቺን ከሚመራበት ቃሉ፣ ትዳራችሁን ከሚያስተዳድርበት ሕጉ ከተለየ አሁኑኑ እዚሁ ጋር አቁሚ!

እህትዓለሜ! ሆዳደሮች በጥናትና ምርምር ሰበብ ወርክሾፕና መድረክ በማሰናዳት በሚጣልላቸው ቅንጥብጣቢ የታወሩ ጥቂቶች ለትንሿ ቤተክርስትያን (ለትዳር/ ለቤተሰብ) እያሰቡላት አይደለምና እንዲህ አልኩሽ!

ይህን ስልሽ በምናምናቸው በኩል የሚሠሩ በርካታ ሸፍጦችን መርምሬ፣ ጥቂት የማይባሉ ሴራዎችን ታዝቤ፣ እኔም ራሴ ባመንኳቸውና ባጎረስኳቸው በእምነት በሚመስሉኝ ወንድሞችና አባቶች ተበድዬ (ትዳሬ ፈርሶ) በከባዱ መንገድ ገንዘብ ባደረግኩት ጥበብ ነው።

ታናሼ! አቺን ደግሞ እወድሻለሁና ይህ እንዲኾንብሽ አልፈቅድምና አስቀድሜ እንዲህ አልኩሽ! እርሱ ማንም ቢኾን ማንም ታውቂያለሽ? ማንም!

👉 የወለደች እናትሽ፣
👉 ወንድም እህትሽ፣
👉 መንፈሳዊ አባትሽም ቢኾን አንቺን ከአካልሽ፣ ከአባወራው ራስሽ ከሚለይሽ ተለይ!

ትዳር ቤተሰብና ልጆች ላይ የታቀደ ጥፋት አለ!
ሴትና ወንድ ዳግም እንዳይተማመኑ፣ በትዳር እንዳያምኑ፣ ልጅ ከመውለድ ይልቅ መዳራትን እንዲመርጡ፣ ከኾነም ዲቃላ ጎትው እንዲያመጡ በዚህም ትውልዱን መረን ለማውጣት እየተዘረጋ ያለ!

እህትዓለሜ!
🌟 ስወድሽ ከባልሽ ተጣበቂ!
🌟 ባይጥምሽም ቢመርሽም መድኃኒትሽ ነውና የእርሱን ቃል ጠብቂ!
🌟 ቅዱስ መጽሐፍ እንደሚልሽ ታዘዢ!
🌟 እንዲያ ባልታዘዝሽበት ስጦታውም፣ መስዋዕቱም፣ መባውም፣ አገልግሎቱም ከንቱ ነውና!

ከዚህ ውጪ እናቅልሻለን ብለው የሚመጡት ሁሉ ደግሞ የሰይጣንና የካርል ማርክስ የግብር ልጆች፣ ምንደኛ ሆዳደሮች ናቸውና፦ አንተ ሰይጣን ከፊቴ ዘወር በል ማለቱንም እወቁበት!

እወድሻለሁና እንዲህ አልኩሽ!