የኢሳያስ የ32 አመት የአገዛዝ ዘመን ኤርትራ ነፃነቷን ካወጀች በኋላ የህገመንግስት መዋቅር የላትም ብሏል። ሕገ መንግሥት የለም፣ ፓርላማ የለም፣ሲቪል ሰርቪስ የለም። ኤርትራ ውስጥ ህግ አስፈፃሚ፣ ህግ አውጭ እና ህጋዊ ተርጓሚ አንድ ብቻ ነው፣እሱም ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ብቻ ነው ያላል አስተያየቱ።
በኤርትራ ወታደራዊ አገልግሎትም በግዴታ እና የአገልግሎት ዘመኑ በጊዜ ያልተገደበ ነው።
ወጣት ኤርትራዊያን ከፕሬዚዳንቱ ጦር ለማምጣት እድሜ ልካቸውን በሽሽት ይኖራሉ።
በዚህም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የኤርትራ ወጣቶቾ በተለይ ወንዶች በህገ ወጥ መንገድ ወደ ጎረቤት ሀገራት እና አውሮፓ የሚሰደዱ እና ህይወታቸውን የሚያጠፉ ብዙ ናቸው።
ጦርነት የኤርትራ መንግስት ዋና የገቢ ምንጩ መሆኑን ዘገባው ያትታል። እዚህም እዚያም የሚቀሰቅስ ግጭት፣ አማፂያንን፣ወይም መንግስታትን በመደገፍ ጦርነትን ያባብሳል።
ዛሬ ኢሳያስ እንደገና ሊገመት በሚችል መልኩ አጥፊ በሆኑ እንቅስቃሴዎች ላይ ተጠምዷል።
በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል የተፈጠረው ጦርነት በፕርቶሪያ ስምምነት ቢቋጭም ኢሳያስ አፈወርቂ በዚህ ስምምነት ደስተኛ አይደለም።
በዚህም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ድጋሚ ግጭት እንዲቀሰቀስ እየሰራ ነው፣አሁኑኑ እርምጃ መውሰድ ይገባል" ይላል አስተያየት ገፁ።